4 days ago
የአረንጓዴ ዐሻራ የሰባት ዓመታት ሰባት አንኳር ስኬቶች
*************
አረንጓዴ ዐሻራ በኢትዮጵያ ምድር ከተጀመረበት ጊዜ አንስቶ ባለፉት ሰባት ዓመታት፣ ሀገራችንን ከአፈር መሸርሸር እና ከበረሃማነት የመታደግ ሀገራዊ ራዕይ ብቻ ሳይሆን፤ የምድርን ሕይወት የሚያድስ፣ የዜጎችን ሥነ-ልቦናዊ አስተሳሰብ የሚቀርጽ እና ኢኮኖሚያዊ አቅም የሚገነባ ታላቅ ሕዝባዊ ንቅናቄ ሆኖ ዘልቋል።
ይህ ሀገራዊ የሕልውና ጥረት ከሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ ስትራቴጂዎች ጋር ተናብቦ ባለፉት ሰባት ዓመታት ያስመዘገባቸው ሰባት ዋና ዋና ተጨባጭ ስኬቶች እንደሚከተለው ተተንትነዋል።
1. የችግኝ ብዛትን ከጽድቀት ምጣኔ ጋር ያጣመረ አዲስ ታሪካዊ ሽግግር
ባለፉት ሰባት ዓመታት በቢሊዮኖች የሚቆጠሩ ችግኞች መተከላቸው ብቻ ሳይሆን፣ የተከላው ዋና ትኩረት ወደ ጥራት እና ድኅረ-ተከላ እንክብካቤ በማደጉ የችግኞች ጽድቀት ምጣኔ ከ80 በመቶ በላይ ማደግ ችሏል።
ይህም ቀደም ሲል የነበረውን "መተከል እንጂ አለመጽደቅ" የሚል የብክነት ታሪክን በመቀየር በቆላ እና በደጋ አካባቢዎች የተጎዱ መሬቶች በፍጥነት አረንጓዴ እንዲለብሱ እና ሥነ-ምኅዳራዊ ሚዛን እንዲጠበቅ አድርጓል።
2. ከአካባቢ ጥበቃ ወደ የምግብ ዋስትና የተደረገ መዋቅራዊ የኢኮኖሚ ሽግግር
አረንጓዴ ዐሻራ ከተፈጥሮ የደን ዛፎች ባሻገር እንደ አቮካዶ፣ ማንጎ፣ ፓፓያ፣ አፕል እና ቡና ያሉ ፍሬያማ ተክሎችን በስፋት አካትቷል።
ይህ ስትራቴጂያዊ እርምጃ ፕሮጀክቱን ከአካባቢ ጥበቃ ባለፈ የቤተሰብ የምግብ ዋስትናን የሚያረጋግጥ እና አባወራዎችን የገበያ ተጠቃሚ የሚያደርግ፣ ብሎም የሀገራችን የግብርና ምርት የወጪ ንግድ የሚያሳድግ የኢኮኖሚ ሞተር አድርጎታል።
ይህም የአካባቢ ጥበቃን ከዜጎች የዕለት ተዕለት ኑሮ ማሻሻል ግብ ጋር በማስተሳሰር ዘላቂነቱ የተረጋገጠ የልማት ምሰሶ እንዲሆን አስችሎታል።
3. የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ግንባታ እና የወጣቶች የሥራ ዕድል ፈጠራ
በመላ ሀገራችን የተቋቋሙት በዐሥር ሺዎች የሚቆጠሩ የችግኝ ማፍያ ጣቢያዎች ለብዙ ዜጎች፣ በተለይም ለወጣቶች እና ለሴቶች አዲስ እና ዘላቂ የገቢ ምንጭ ሆነዋል።
ችግኝ ማፍላት፣ መንከባከብ እና ለገበያ ማቅረብ በራሱ አዲስ የኢንቨስትመንት ዘርፍ እና የሥራ ዕድል በመፍጠር፣ የሀገራችንን የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ጅማሮ በጠንካራ መሠረት ላይ አኑሮታል።
ችግኞች ከተተከሉ በኋላ የሚደረገው ጥበቃ እና ክብካቤም በርካታ ወጣቶችን ተጠቃሚ ያደረገ ቋሚ የሥራ ዘርፍ መሆን ችሏል።
4. የውኃ ሀብት እና የታላላቅ ሀገራዊ የልማት ፕሮጀክቶች ዋስትና
በስፋት የተከናወነው የደን ልማት እና የአፈር ጥበቃ ሥራ የአፈር መሸርሸርን በመቀነስ፣ እንደ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ያሉ ሀገራዊ የሃይድሮ ኤሌክትሪክ ማመንጫዎች በደለል እንዳይሞሉ የመከላከል ታሪካዊ ሚና ተጫውቷል።
በተጨማሪም የከርሰ ምድር ውኃ መጠን እንዲያገግም እና የደረቁ የምንጭ ውኃዎች መልሰው እንዲፈልቁ በማድረግ አስተማማኝ የውኃ ዋስትናን እያረጋገጠ ይገኛል።
ይህ ታላላቅ መሠረተ ልማቶችን የመጠበቅ አቅም ለኢትዮጵያ ብልጽግና ብቻ ሳይሆን፣ ሀገራችን የውኃ ምንጭ ለሆነችላቸው የታችኛው ተፋሰስ ሀገራት ጭምር ትልቅ ትሩፋት ነው።
5. አረንጓዴ ዲፕሎማሲ እና የቀጣናዊ ትሥሥር ማጠናከሪያ
ኢትዮጵያ ያዘጋጀቻቸውን ችግኞች እንደ ጂቡቲ፣ ሶማሊያ፣ ደቡብ ሱዳን እና ኬንያ ላሉት ጎረቤት ሀገራት በማጋራት፣ የምሥራቅ አፍሪካን እና የአፍሪካ ቀንድን የቀጣና አየር ንብረት ለውጥ ተግዳሮት በጋራ የመከላከል መሪነት ሚናዋን በተግባር አሳይታለች።
ይህም አረንጓዴ ዐሻራን የድንበር ተሻጋሪ ዲፕሎማሲ፣ የቀጠናው ሰላም እና የጋራ ልማት መሣሪያ አድርጎታል።
በርካታ የአፍሪካ ሀገራትም የኢትዮጵያን ፈለግ በመከተል የአረንጓዴ ልማትን በሀገሮቻቸው እያስፋፉ ይገኛሉ።
ከዚህ ባሻገር፣ ኢትዮጵያ ባመጣቻቸው ተጨባጭ ስኬቶች “ዘላቂ የደን ልማት አያያዝ እና አጠቃቀም” በሚል ዘርፍ ከዓለም የምግብ እና እርሻ ድርጅት (FAO) ከፍተኛ እውቅናን አግኝታለች።
6. የከተሞች ሥነ-ምኅዳር መታደስ እና የኮሪደር ልማት ውበት
አረንጓዴ ዐሻራ በገጠር ተራራዎች ብቻ ተወስኖ ሳይቀር ወደ ከተሞች በመግባት የዘመናዊ ፓርኮች ግንባታ፣ የከተማ አረንጓዴ ልማት እና አሁን ላይ በስፋት እየተተገበረ ላለው የኮሪደር ልማት ዋነኛ አካል ሆኗል።
ይህም የከተሞችን የአየር ጥራት በከፍተኛ ደረጃ ከመጨመሩም በላይ፣ የሥነ-ሕይወት ስብጥርን ወደ ነበረበት በመመለስ እና ለዜጎች ምቹ የመዝናኛ እና የኑሮ አካባቢን በመፍጠር የከተሞቻችንን ገጽታ ሙሉ በሙሉ በመለወጥ ላይ ይገኛል።
7. ሕዝባዊ ንቅናቄ እና የዜግነት አገልግሎት ባህል ግንባታ
በአንድ ጀምበር በመቶ ሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎች በነቂስ ወጥተው ችግኝ የመተከል ልምዳቸው፣ የአካባቢ ጥበቃን ከዘመቻነት አውጥቶ የባህል እና የዜግነት ግዴታ አካል አድርጎታል።
ይህም የሕዝባዊ ወንድማማችነትን ያጠናከረ እና የአካባቢ ጥበቃ ግንዛቤን በማሳደግ ለቀጣዩ ትውልድ የሚሻገር እጅግ ግዙፍ ማኅበራዊ እና ሥነ-ልቦናዊ ስኬት ነው።
በአጠቃላይ አረንጓዴ ዐሻራ ባለፉት ሰባት ዓመታት የተፈጥሮ ሀብታችንን ከመመለስ አልፎ ሀገራዊ አንድነትን ያጠናከረ፣ የማክሮ ኢኮኖሚ አቅማችንን የገነባ እና ኢትዮጵያን በዓለም አቀፍ መድረክ ለአየር ንብረት ለውጥ መፍትሔ አቅራቢ ሀገር ያደረገ አንጸባራቂ አዲስ የታሪክ ምዕራፍ ነው።
በለሚ ታደሰ
#ethiopia #ebc #greenlegacy #climateaction #greendiplomacy #greeneconomy
*************
አረንጓዴ ዐሻራ በኢትዮጵያ ምድር ከተጀመረበት ጊዜ አንስቶ ባለፉት ሰባት ዓመታት፣ ሀገራችንን ከአፈር መሸርሸር እና ከበረሃማነት የመታደግ ሀገራዊ ራዕይ ብቻ ሳይሆን፤ የምድርን ሕይወት የሚያድስ፣ የዜጎችን ሥነ-ልቦናዊ አስተሳሰብ የሚቀርጽ እና ኢኮኖሚያዊ አቅም የሚገነባ ታላቅ ሕዝባዊ ንቅናቄ ሆኖ ዘልቋል።
ይህ ሀገራዊ የሕልውና ጥረት ከሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ ስትራቴጂዎች ጋር ተናብቦ ባለፉት ሰባት ዓመታት ያስመዘገባቸው ሰባት ዋና ዋና ተጨባጭ ስኬቶች እንደሚከተለው ተተንትነዋል።
1. የችግኝ ብዛትን ከጽድቀት ምጣኔ ጋር ያጣመረ አዲስ ታሪካዊ ሽግግር
ባለፉት ሰባት ዓመታት በቢሊዮኖች የሚቆጠሩ ችግኞች መተከላቸው ብቻ ሳይሆን፣ የተከላው ዋና ትኩረት ወደ ጥራት እና ድኅረ-ተከላ እንክብካቤ በማደጉ የችግኞች ጽድቀት ምጣኔ ከ80 በመቶ በላይ ማደግ ችሏል።
ይህም ቀደም ሲል የነበረውን "መተከል እንጂ አለመጽደቅ" የሚል የብክነት ታሪክን በመቀየር በቆላ እና በደጋ አካባቢዎች የተጎዱ መሬቶች በፍጥነት አረንጓዴ እንዲለብሱ እና ሥነ-ምኅዳራዊ ሚዛን እንዲጠበቅ አድርጓል።
2. ከአካባቢ ጥበቃ ወደ የምግብ ዋስትና የተደረገ መዋቅራዊ የኢኮኖሚ ሽግግር
አረንጓዴ ዐሻራ ከተፈጥሮ የደን ዛፎች ባሻገር እንደ አቮካዶ፣ ማንጎ፣ ፓፓያ፣ አፕል እና ቡና ያሉ ፍሬያማ ተክሎችን በስፋት አካትቷል።
ይህ ስትራቴጂያዊ እርምጃ ፕሮጀክቱን ከአካባቢ ጥበቃ ባለፈ የቤተሰብ የምግብ ዋስትናን የሚያረጋግጥ እና አባወራዎችን የገበያ ተጠቃሚ የሚያደርግ፣ ብሎም የሀገራችን የግብርና ምርት የወጪ ንግድ የሚያሳድግ የኢኮኖሚ ሞተር አድርጎታል።
ይህም የአካባቢ ጥበቃን ከዜጎች የዕለት ተዕለት ኑሮ ማሻሻል ግብ ጋር በማስተሳሰር ዘላቂነቱ የተረጋገጠ የልማት ምሰሶ እንዲሆን አስችሎታል።
3. የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ግንባታ እና የወጣቶች የሥራ ዕድል ፈጠራ
በመላ ሀገራችን የተቋቋሙት በዐሥር ሺዎች የሚቆጠሩ የችግኝ ማፍያ ጣቢያዎች ለብዙ ዜጎች፣ በተለይም ለወጣቶች እና ለሴቶች አዲስ እና ዘላቂ የገቢ ምንጭ ሆነዋል።
ችግኝ ማፍላት፣ መንከባከብ እና ለገበያ ማቅረብ በራሱ አዲስ የኢንቨስትመንት ዘርፍ እና የሥራ ዕድል በመፍጠር፣ የሀገራችንን የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ጅማሮ በጠንካራ መሠረት ላይ አኑሮታል።
ችግኞች ከተተከሉ በኋላ የሚደረገው ጥበቃ እና ክብካቤም በርካታ ወጣቶችን ተጠቃሚ ያደረገ ቋሚ የሥራ ዘርፍ መሆን ችሏል።
4. የውኃ ሀብት እና የታላላቅ ሀገራዊ የልማት ፕሮጀክቶች ዋስትና
በስፋት የተከናወነው የደን ልማት እና የአፈር ጥበቃ ሥራ የአፈር መሸርሸርን በመቀነስ፣ እንደ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ያሉ ሀገራዊ የሃይድሮ ኤሌክትሪክ ማመንጫዎች በደለል እንዳይሞሉ የመከላከል ታሪካዊ ሚና ተጫውቷል።
በተጨማሪም የከርሰ ምድር ውኃ መጠን እንዲያገግም እና የደረቁ የምንጭ ውኃዎች መልሰው እንዲፈልቁ በማድረግ አስተማማኝ የውኃ ዋስትናን እያረጋገጠ ይገኛል።
ይህ ታላላቅ መሠረተ ልማቶችን የመጠበቅ አቅም ለኢትዮጵያ ብልጽግና ብቻ ሳይሆን፣ ሀገራችን የውኃ ምንጭ ለሆነችላቸው የታችኛው ተፋሰስ ሀገራት ጭምር ትልቅ ትሩፋት ነው።
5. አረንጓዴ ዲፕሎማሲ እና የቀጣናዊ ትሥሥር ማጠናከሪያ
ኢትዮጵያ ያዘጋጀቻቸውን ችግኞች እንደ ጂቡቲ፣ ሶማሊያ፣ ደቡብ ሱዳን እና ኬንያ ላሉት ጎረቤት ሀገራት በማጋራት፣ የምሥራቅ አፍሪካን እና የአፍሪካ ቀንድን የቀጣና አየር ንብረት ለውጥ ተግዳሮት በጋራ የመከላከል መሪነት ሚናዋን በተግባር አሳይታለች።
ይህም አረንጓዴ ዐሻራን የድንበር ተሻጋሪ ዲፕሎማሲ፣ የቀጠናው ሰላም እና የጋራ ልማት መሣሪያ አድርጎታል።
በርካታ የአፍሪካ ሀገራትም የኢትዮጵያን ፈለግ በመከተል የአረንጓዴ ልማትን በሀገሮቻቸው እያስፋፉ ይገኛሉ።
ከዚህ ባሻገር፣ ኢትዮጵያ ባመጣቻቸው ተጨባጭ ስኬቶች “ዘላቂ የደን ልማት አያያዝ እና አጠቃቀም” በሚል ዘርፍ ከዓለም የምግብ እና እርሻ ድርጅት (FAO) ከፍተኛ እውቅናን አግኝታለች።
6. የከተሞች ሥነ-ምኅዳር መታደስ እና የኮሪደር ልማት ውበት
አረንጓዴ ዐሻራ በገጠር ተራራዎች ብቻ ተወስኖ ሳይቀር ወደ ከተሞች በመግባት የዘመናዊ ፓርኮች ግንባታ፣ የከተማ አረንጓዴ ልማት እና አሁን ላይ በስፋት እየተተገበረ ላለው የኮሪደር ልማት ዋነኛ አካል ሆኗል።
ይህም የከተሞችን የአየር ጥራት በከፍተኛ ደረጃ ከመጨመሩም በላይ፣ የሥነ-ሕይወት ስብጥርን ወደ ነበረበት በመመለስ እና ለዜጎች ምቹ የመዝናኛ እና የኑሮ አካባቢን በመፍጠር የከተሞቻችንን ገጽታ ሙሉ በሙሉ በመለወጥ ላይ ይገኛል።
7. ሕዝባዊ ንቅናቄ እና የዜግነት አገልግሎት ባህል ግንባታ
በአንድ ጀምበር በመቶ ሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎች በነቂስ ወጥተው ችግኝ የመተከል ልምዳቸው፣ የአካባቢ ጥበቃን ከዘመቻነት አውጥቶ የባህል እና የዜግነት ግዴታ አካል አድርጎታል።
ይህም የሕዝባዊ ወንድማማችነትን ያጠናከረ እና የአካባቢ ጥበቃ ግንዛቤን በማሳደግ ለቀጣዩ ትውልድ የሚሻገር እጅግ ግዙፍ ማኅበራዊ እና ሥነ-ልቦናዊ ስኬት ነው።
በአጠቃላይ አረንጓዴ ዐሻራ ባለፉት ሰባት ዓመታት የተፈጥሮ ሀብታችንን ከመመለስ አልፎ ሀገራዊ አንድነትን ያጠናከረ፣ የማክሮ ኢኮኖሚ አቅማችንን የገነባ እና ኢትዮጵያን በዓለም አቀፍ መድረክ ለአየር ንብረት ለውጥ መፍትሔ አቅራቢ ሀገር ያደረገ አንጸባራቂ አዲስ የታሪክ ምዕራፍ ነው።
በለሚ ታደሰ
#ethiopia #ebc #greenlegacy #climateaction #greendiplomacy #greeneconomy
4 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ከኦገስት 1 ቀን 2026 ጀምሮ ከሰሃራ በታች ባሉ 25 የአፍሪካ ሀገራት በሚገኙ ዲፕሎማሲያዊ ሚሲዮኖች የሚሰጠውን መደበኛ የቪዛ ማስተናገጃ አገልግሎት ማቋረጡን አስታውቋል። የትራምፕ አስተዳደር ይህንን ውሳኔ በቅርብ ታሪክ ውስጥ ከተደረጉት የአሜሪካ ዲፕሎማሲያዊ የቪዛ አገልግሎቶች ትልቁ የማሻሻያ መርሃ ግብር ሲል ገልጾታል።
በአዲሱ አሰራር መሰረት የቪዛ አመልካቾች ከዚህ በኋላ በአቅራቢያቸው በሚገኝ የአሜሪካ ኤምባሲ ወይም ቆንስላ ጽህፈት ቤት ቀጠሮ መያዝም ሆነ የቪዛ ሂደታቸውን ማጠናቀቅ አይችሉም። ከዚህ ይልቅ በአህጉሪቱ ወደተመደቡ 20 ቀጠናዊ ማስተናገጃ ማዕከላት እንዲያቀኑ ይደረጋል።
የቪዛ አገልግሎታቸው የተቋረጠባቸው 25ቱ ሚሲዮኖች አቡጃ (ናይጄሪያ)፣ አንታናናሪቮ (ማዳጋስካር)፣ አስመራ (ኤርትራ)፣ ባማኮ (ማሊ)፣ ባንጁል (ጋምቢያ)፣ ብራዛቪል (የኮንጎ ሪፐብሊክ)፣ ቡጁምቡራ (ብሩንዲ)፣ ኮናክሪ (ጊኒ)፣ ኮቶኑ (ቤኒን)፣ ደርባን (ደቡብ አፍሪካ)፣ ፍሪታውን (ሴራሊዮን)፣ ጋቦሮኔ (ቦትስዋና)፣ ሃራሬ (ዚምባብዌ)፣ ጁባ (ደቡብ ሱዳን)፣ ሊብረቪል (ጋቦን)፣ ሊሎንግዌ (ማላዊ)፣ ሉሳካ (ዛምቢያ)፣ ማፑቶ (ሞዛምቢክ)፣ ማሴሩ (ሌሴቶ)፣ ምባባኔ (ኤስዋቲኒ)፣ ንጃሜና (ቻድ)፣ ኒያሜይ (ኒጀር)፣ ኑዋክሾት (ሞሪታኒያ)፣ ዋጋዱጉ (ቡርኪና ፋሶ) እና ዊንድሆክ (ናሚቢያ) ናቸው። በደቡብ አፍሪካ ደርባን የሚገኘው የቪዛ ማዕከል ቢዘጋም፣ በኬፕታውን የሚሰጠው ተመሳሳይ አገልግሎት ግን ሳይቋረጥ እንደሚቀጥል ተገልጿል።
20ዎቹ አዳዲስ ቀጠናዊ ማስተናገጃ ማዕከላት በአቢጃን፣ አክራ፣ አዲስ አበባ፣ ኬፕታውን (ደቡብ አፍሪካ)፣ ዳካር፣ ዳሬሰላም፣ ጅቡቲ፣ ጆሃንስበርግ፣ ካምፓላ፣ ኪጋሊ፣ ኪንሻሳ፣ ሌጎስ፣ ሎሜ፣ ሉዋንዳ፣ ማላቦ፣ ሞንሮቪያ፣ ናይሮቢ፣ ፖርት ሉዊስ፣ ፕራያ እና ያውንዴ የሚገኙ ይሆናሉ። እያንዳንዱ ማዕከል በርካታ ጎረቤት ሀገራትን የሚያስተናግድ ሲሆን፣ ለምሳሌ ከማሊ የሚመጡ አመልካቾች በዳካር (ሴኔጋል)፣ እንዲሁም ከቤኒን እና ኒጀር የሚመጡት ደግሞ በሎሜ (ቶጎ) የቪዛ ሂደታቸውን እንዲያከናውኑ ይመራሉ።
ሚኒስቴሩ ውሳኔውን የትራምፕ አስተዳደር ብሔራዊ ደህንነትን ለማጠናከር፣ የማጣራት ሂደቶችን ወጥ ለማድረግ፣ የመንግስት ወጪን ለመቀነስ እና የአሰራር ቅልጥፍናን ለማሻሻል ከሚያደርገው ጥረት አንዱ አካል መሆኑን አብራርቷል። ተመሳሳይ የውህደት ስራዎች በሌሎች የአፍሪካ ሀገራት እና በአውሮፓ ክፍሎች ቀደም ሲል መከናወናቸውን የገለጸው ሚኒስቴሩ፣ ፕሬዝዳንት ትራምፕ ብሔራዊ ደህንነትን በማጠናከር እና የመንግስትን ብክነት በመቀነስ አሜሪካን እና አሜሪካውያንን እያስቀደሙ ነው ብሏል።
ይህ ማሻሻያ ከሰሃራ በታች ባሉ የአፍሪካ ሀገራት የቪዛ ማመልከቻዎችን የሚያስተናግዱ የአሜሪካ ሚሲዮኖችን ቁጥር ከ50 ገደማ ወደ 20 ዝቅ ያደርገዋል። ይህ በአመልካቾች ላይ ጉልህ የሆነ ተግባራዊ ተጽእኖ የሚያሳድር ሲሆን፣ የአገር ውስጥ የቪዛ አገልግሎት በተቋረጠባቸው ሀገራት የሚገኙ ዜጎች በአካል ለሚደረግ ቃለ ምልልስ እና የጣት አሻራ (ባዮሜትሪክ) ምዝገባ አለም አቀፍ ድንበሮችን አቋርጠው ለመጓዝ ስለሚገደዱ ለተጨማሪ የትራንስፖርት እና የማረፊያ ወጪዎች ይዳረጋሉ።
በአዲሱ አሰራር መሰረት የቪዛ አመልካቾች ከዚህ በኋላ በአቅራቢያቸው በሚገኝ የአሜሪካ ኤምባሲ ወይም ቆንስላ ጽህፈት ቤት ቀጠሮ መያዝም ሆነ የቪዛ ሂደታቸውን ማጠናቀቅ አይችሉም። ከዚህ ይልቅ በአህጉሪቱ ወደተመደቡ 20 ቀጠናዊ ማስተናገጃ ማዕከላት እንዲያቀኑ ይደረጋል።
የቪዛ አገልግሎታቸው የተቋረጠባቸው 25ቱ ሚሲዮኖች አቡጃ (ናይጄሪያ)፣ አንታናናሪቮ (ማዳጋስካር)፣ አስመራ (ኤርትራ)፣ ባማኮ (ማሊ)፣ ባንጁል (ጋምቢያ)፣ ብራዛቪል (የኮንጎ ሪፐብሊክ)፣ ቡጁምቡራ (ብሩንዲ)፣ ኮናክሪ (ጊኒ)፣ ኮቶኑ (ቤኒን)፣ ደርባን (ደቡብ አፍሪካ)፣ ፍሪታውን (ሴራሊዮን)፣ ጋቦሮኔ (ቦትስዋና)፣ ሃራሬ (ዚምባብዌ)፣ ጁባ (ደቡብ ሱዳን)፣ ሊብረቪል (ጋቦን)፣ ሊሎንግዌ (ማላዊ)፣ ሉሳካ (ዛምቢያ)፣ ማፑቶ (ሞዛምቢክ)፣ ማሴሩ (ሌሴቶ)፣ ምባባኔ (ኤስዋቲኒ)፣ ንጃሜና (ቻድ)፣ ኒያሜይ (ኒጀር)፣ ኑዋክሾት (ሞሪታኒያ)፣ ዋጋዱጉ (ቡርኪና ፋሶ) እና ዊንድሆክ (ናሚቢያ) ናቸው። በደቡብ አፍሪካ ደርባን የሚገኘው የቪዛ ማዕከል ቢዘጋም፣ በኬፕታውን የሚሰጠው ተመሳሳይ አገልግሎት ግን ሳይቋረጥ እንደሚቀጥል ተገልጿል።
20ዎቹ አዳዲስ ቀጠናዊ ማስተናገጃ ማዕከላት በአቢጃን፣ አክራ፣ አዲስ አበባ፣ ኬፕታውን (ደቡብ አፍሪካ)፣ ዳካር፣ ዳሬሰላም፣ ጅቡቲ፣ ጆሃንስበርግ፣ ካምፓላ፣ ኪጋሊ፣ ኪንሻሳ፣ ሌጎስ፣ ሎሜ፣ ሉዋንዳ፣ ማላቦ፣ ሞንሮቪያ፣ ናይሮቢ፣ ፖርት ሉዊስ፣ ፕራያ እና ያውንዴ የሚገኙ ይሆናሉ። እያንዳንዱ ማዕከል በርካታ ጎረቤት ሀገራትን የሚያስተናግድ ሲሆን፣ ለምሳሌ ከማሊ የሚመጡ አመልካቾች በዳካር (ሴኔጋል)፣ እንዲሁም ከቤኒን እና ኒጀር የሚመጡት ደግሞ በሎሜ (ቶጎ) የቪዛ ሂደታቸውን እንዲያከናውኑ ይመራሉ።
ሚኒስቴሩ ውሳኔውን የትራምፕ አስተዳደር ብሔራዊ ደህንነትን ለማጠናከር፣ የማጣራት ሂደቶችን ወጥ ለማድረግ፣ የመንግስት ወጪን ለመቀነስ እና የአሰራር ቅልጥፍናን ለማሻሻል ከሚያደርገው ጥረት አንዱ አካል መሆኑን አብራርቷል። ተመሳሳይ የውህደት ስራዎች በሌሎች የአፍሪካ ሀገራት እና በአውሮፓ ክፍሎች ቀደም ሲል መከናወናቸውን የገለጸው ሚኒስቴሩ፣ ፕሬዝዳንት ትራምፕ ብሔራዊ ደህንነትን በማጠናከር እና የመንግስትን ብክነት በመቀነስ አሜሪካን እና አሜሪካውያንን እያስቀደሙ ነው ብሏል።
ይህ ማሻሻያ ከሰሃራ በታች ባሉ የአፍሪካ ሀገራት የቪዛ ማመልከቻዎችን የሚያስተናግዱ የአሜሪካ ሚሲዮኖችን ቁጥር ከ50 ገደማ ወደ 20 ዝቅ ያደርገዋል። ይህ በአመልካቾች ላይ ጉልህ የሆነ ተግባራዊ ተጽእኖ የሚያሳድር ሲሆን፣ የአገር ውስጥ የቪዛ አገልግሎት በተቋረጠባቸው ሀገራት የሚገኙ ዜጎች በአካል ለሚደረግ ቃለ ምልልስ እና የጣት አሻራ (ባዮሜትሪክ) ምዝገባ አለም አቀፍ ድንበሮችን አቋርጠው ለመጓዝ ስለሚገደዱ ለተጨማሪ የትራንስፖርት እና የማረፊያ ወጪዎች ይዳረጋሉ።
9 days ago
ሻዕቢያ ሕዝቡን ለእንግልትና ለስደት ዳርጓል፤ ኢትዮጵያ ከ400 ሺህ በላይ ኤርትራውያንን ተቀብላ አስጠልላለች
ሻዕቢያ ስልጣን ከያዘበት ጊዜ ጀምሮ ከ30 ዓመታት በላይ በኤርትራ ሕዝብ ላይ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ቀውሶችን አስከትሏል፡፡
የኤርትራ ሕዝብ ከሰላሳ ዓመታት በላይ በተደረገ የትጥቅ ትግል ነጻነት ተጎናጸፍኩ ቢልም፣ የነጻነት ትግሉን የመራው የሻዕቢያ መንግሥት፣ ሀገሪቱን በብቸኝነት እያስተዳደረ ይገኛል።
ይህ አካሄድም ኤርትራን ወደ ተወሳሰበ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ቀውስ ውስጥ የከተታት መሆኑን ወደ ኢትዮጵያ ተሰደው የመጡ ኤርትራውያን፣ በርካታ ዓለም አቀፍ ተቋማትና የፖለቲካ ተንታኞች ይስማማሉ።
በኤርትራ የሚታየው ዋነኛው ቀውስ ከፖለቲካዊ መዋቅሩ ጋር የተያያዘ ነው። በፈረንጆቹ 1997 የሀገሪቱ ብሔራዊ ምክር ቤት ያጸደቀውና በርካታ የሲቪል መብቶችን የያዘው ህገ-መንግሥት እስካሁን ድረስ ተግባራዊ አልተደረገም፡፡
በሀገሪቱ ውስጥ የአንድ ፓርቲ አምባገነንነት ነው ያለው፡፡ ከሻዕቢያ ውጭ ሌላ ማንኛውም የፖለቲካ ፓርቲ እንዳይቋቋም በህግ የተከለከለ ሲሆን፣ ሀገራዊ ምርጫም ተካሂዶ አያውቅም።
ከፈረንጆቹ 2001 ጀምሮ የግል መገናኛ ብዙሃን ሙሉ በሙሉ የተዘጉ ሲሆን÷ መንግሥትን የተቹ ከፍተኛ ባለስልጣናት፣ ጋዜጠኞችና የሃይማኖት መሪዎች ያለ ፍርድ ቤት ትዕዛዝ በእስር ላይ ይገኛሉ። ለሥርዓቱ ታግለው በእስር ላይ ሕይወታቸውን ያጡም በርካቶች ናቸው፡፡
ህግ አውጪ፣ ህግ ተርጓሚና ህግ አስፈጻሚው አካል በአንድ ግለሰብ ማለትም በኢሳያስ አፈወርቂ ቁጥጥር ሥር መውደቃቸው የፍትህ ሥርዓቱን አዳክሞታል።
የኤርትራ መንግሥት ራስን መርህ ያደረገ የኢኮኖሚ ፖሊሲ እከተላለሁ ቢልም በተግባር ግን ኢኮኖሚው እንዲዳከምና የሕዝቡ የመግዛት አቅም እንዲደቅ አድርጓል።
የግሉ ዘርፍ እጅግ የተገደበ ሲሆን÷ አብዛኛው የንግድና የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ በሻዕቢያ የንግድ ተቋማትና በጦር አዛዦች ቁጥጥር ስር ነው። ይህ የመንግሥት ሞኖፖሊም ጤናማ የገበያ ውድድር እንዳይኖር አድርጓል።
በፖለቲካዊ አለመረጋጋት፣ በሕግ የበላይነት እጥረትና በውጭ ምንዛሪ ቁጥጥር ምክንያት የውጭ ሀገር ኩባንያዎች በሀገሪቱ ኢንቨስት ማድረግ አይፈልጉም።
በሀገሪቱ የተጠናከረ የኢኮኖሚ ማሻሻያ ባለመኖሩ የኤሌክትሪክ ኃይል፣ የንጹህ መጠጥ ውሃ፣ የቴሌኮሙኒኬሽንና የትራንስፖርት አገልግሎቶች ደርግ ጥሏቸው እንደሄደ ዝቅተኛ ደረጃ ላይ ይገኛሉ።
ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ጫናው በቀጥታ የኤርትራን ህዝብ ስነ-ልቦናዊና ሥነ-ሕዝባዊ መዋቅር አናግቶታል።
የግጭት ስነልቦና ያልተለየው ሻዕቢያ፣ ወጣቶች በውትድርና እንዲያገለግሉ ግዴታ ይጥላል፡፡ ወጣቶችም በሳዋ ወታደራዊ ማሰልጠኛ ስልጠናቸውን ከጨረሱ በኋላ ለዓመታት በዝቅተኛ ክፍያ በውትድርናና በግዳጅ ስራ ላይ እንዲሰማሩ ይደረጋል። ይህ አሰራር የወጣቶችን የወደፊት ተስፋ ያጨለመ ሆኗል።
ከዚህ የግዳጅ አገልግሎትና ከኢኮኖሚ ችግር ለማምለጥ በየወሩ በሺህ የሚቆጠሩ ወጣቶች ሕይወታቸውን ለአደጋ አጋልጠው ይሰደዳሉ። ይህ ስደት ሀገሪቱን የተማረና አምራች የሰው ኃይል አሳጥቷታል።
አባወራዎች በውትድርና ረጅም ጊዜ ማሳለፋቸውና የወጣቶች በብዛት መሰደድ የኤርትራውያንን ማህበራዊ ትስስርና የቤተሰብ መዋቅር እያፈራረሰው ይገኛል።
ከኤርትራ መገንጠል በኋላ በሀገሪቱ ካለው የፖለቲካና የግዳጅ ውትድርና ሥርዓት ለማምለጥ በ100 ሺህ የሚቆጠሩ ኤርትራውያን ወደ ኢትዮጵያ ተሰደዋል።
ኢትዮጵያ በምስራቅ አፍሪካ በርካታ ስደተኞችን ከሚያስተናግዱ ግንባር ቀደም ሀገራት አንዷ ስትሆን÷ የኤርትራ ስደተኞች ከደቡብ ሱዳንና ከሶማሊያ ቀጥሎ ሦስተኛውን ትልቅ ስብስብ ይይዛሉ።
የኢትዮጵያና የኤርትራ ህዝብ ተመሳሳይ የስነ ልቦና ውቅር፣ ታሪክ፣ ባህልና ኃይማኖት የሚጋሩ ህዝቦች በመሆናቸው፣ ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት ከ400 ሺህ በላይ የኤርትራ ስደተኞችን አስጠልላ ትገኛለች፡፡
ይህ ኢትዮጵያ ለጎረቤት ሀገራት ዜጎች የምታደርገውን ሰብዓዊ መስተንግዶ የሚያሳይ ሲሆን÷ ኤርትራውያንን ጨምሮ ኢትዮጵያ በአጠቃላይ የ1 ነጥብ 3 ሚሊየን ስደተኞች መጠለያ ናት፡፡
በአጠቃላይ ሻዕቢያ ኤርትራን ወደ ተሻለ የዴሞክራሲና የብልጽግና ምዕራፍ ማሸጋገር አልቻለም። ሻዕቢያ እነዚህን ቀውሶች ከራሱ የፖሊሲ ስህተት ይልቅ ከውጭ ሀገራት ጫና፣ ከድንበር አለመወሰንና ከዓለም አቀፍ ማዕቀቦች ጋር ለማያያዝ ይሞክራል፡፡
በሀገር ውስጥ ያለው ነባራዊ ሁኔታ ግን የሕዝቡን ህይወት እጅግ ፈታኝ አድርጎታል።
ኤርትራ ካለችበት ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ቀውስ እንድትወጣ፣ የአንድ ፓርቲ አገዛዝን ወደ ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓት መመለስ፣ የዜጎችን ሰብዓዊ መብቶች ማስከበርና የኢኮኖሚ ማሻሻያዎችን መተግበር የግድ ይላል።
ሻዕቢያ ስልጣን ከያዘበት ጊዜ ጀምሮ ከ30 ዓመታት በላይ በኤርትራ ሕዝብ ላይ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ቀውሶችን አስከትሏል፡፡
የኤርትራ ሕዝብ ከሰላሳ ዓመታት በላይ በተደረገ የትጥቅ ትግል ነጻነት ተጎናጸፍኩ ቢልም፣ የነጻነት ትግሉን የመራው የሻዕቢያ መንግሥት፣ ሀገሪቱን በብቸኝነት እያስተዳደረ ይገኛል።
ይህ አካሄድም ኤርትራን ወደ ተወሳሰበ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ቀውስ ውስጥ የከተታት መሆኑን ወደ ኢትዮጵያ ተሰደው የመጡ ኤርትራውያን፣ በርካታ ዓለም አቀፍ ተቋማትና የፖለቲካ ተንታኞች ይስማማሉ።
በኤርትራ የሚታየው ዋነኛው ቀውስ ከፖለቲካዊ መዋቅሩ ጋር የተያያዘ ነው። በፈረንጆቹ 1997 የሀገሪቱ ብሔራዊ ምክር ቤት ያጸደቀውና በርካታ የሲቪል መብቶችን የያዘው ህገ-መንግሥት እስካሁን ድረስ ተግባራዊ አልተደረገም፡፡
በሀገሪቱ ውስጥ የአንድ ፓርቲ አምባገነንነት ነው ያለው፡፡ ከሻዕቢያ ውጭ ሌላ ማንኛውም የፖለቲካ ፓርቲ እንዳይቋቋም በህግ የተከለከለ ሲሆን፣ ሀገራዊ ምርጫም ተካሂዶ አያውቅም።
ከፈረንጆቹ 2001 ጀምሮ የግል መገናኛ ብዙሃን ሙሉ በሙሉ የተዘጉ ሲሆን÷ መንግሥትን የተቹ ከፍተኛ ባለስልጣናት፣ ጋዜጠኞችና የሃይማኖት መሪዎች ያለ ፍርድ ቤት ትዕዛዝ በእስር ላይ ይገኛሉ። ለሥርዓቱ ታግለው በእስር ላይ ሕይወታቸውን ያጡም በርካቶች ናቸው፡፡
ህግ አውጪ፣ ህግ ተርጓሚና ህግ አስፈጻሚው አካል በአንድ ግለሰብ ማለትም በኢሳያስ አፈወርቂ ቁጥጥር ሥር መውደቃቸው የፍትህ ሥርዓቱን አዳክሞታል።
የኤርትራ መንግሥት ራስን መርህ ያደረገ የኢኮኖሚ ፖሊሲ እከተላለሁ ቢልም በተግባር ግን ኢኮኖሚው እንዲዳከምና የሕዝቡ የመግዛት አቅም እንዲደቅ አድርጓል።
የግሉ ዘርፍ እጅግ የተገደበ ሲሆን÷ አብዛኛው የንግድና የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ በሻዕቢያ የንግድ ተቋማትና በጦር አዛዦች ቁጥጥር ስር ነው። ይህ የመንግሥት ሞኖፖሊም ጤናማ የገበያ ውድድር እንዳይኖር አድርጓል።
በፖለቲካዊ አለመረጋጋት፣ በሕግ የበላይነት እጥረትና በውጭ ምንዛሪ ቁጥጥር ምክንያት የውጭ ሀገር ኩባንያዎች በሀገሪቱ ኢንቨስት ማድረግ አይፈልጉም።
በሀገሪቱ የተጠናከረ የኢኮኖሚ ማሻሻያ ባለመኖሩ የኤሌክትሪክ ኃይል፣ የንጹህ መጠጥ ውሃ፣ የቴሌኮሙኒኬሽንና የትራንስፖርት አገልግሎቶች ደርግ ጥሏቸው እንደሄደ ዝቅተኛ ደረጃ ላይ ይገኛሉ።
ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ጫናው በቀጥታ የኤርትራን ህዝብ ስነ-ልቦናዊና ሥነ-ሕዝባዊ መዋቅር አናግቶታል።
የግጭት ስነልቦና ያልተለየው ሻዕቢያ፣ ወጣቶች በውትድርና እንዲያገለግሉ ግዴታ ይጥላል፡፡ ወጣቶችም በሳዋ ወታደራዊ ማሰልጠኛ ስልጠናቸውን ከጨረሱ በኋላ ለዓመታት በዝቅተኛ ክፍያ በውትድርናና በግዳጅ ስራ ላይ እንዲሰማሩ ይደረጋል። ይህ አሰራር የወጣቶችን የወደፊት ተስፋ ያጨለመ ሆኗል።
ከዚህ የግዳጅ አገልግሎትና ከኢኮኖሚ ችግር ለማምለጥ በየወሩ በሺህ የሚቆጠሩ ወጣቶች ሕይወታቸውን ለአደጋ አጋልጠው ይሰደዳሉ። ይህ ስደት ሀገሪቱን የተማረና አምራች የሰው ኃይል አሳጥቷታል።
አባወራዎች በውትድርና ረጅም ጊዜ ማሳለፋቸውና የወጣቶች በብዛት መሰደድ የኤርትራውያንን ማህበራዊ ትስስርና የቤተሰብ መዋቅር እያፈራረሰው ይገኛል።
ከኤርትራ መገንጠል በኋላ በሀገሪቱ ካለው የፖለቲካና የግዳጅ ውትድርና ሥርዓት ለማምለጥ በ100 ሺህ የሚቆጠሩ ኤርትራውያን ወደ ኢትዮጵያ ተሰደዋል።
ኢትዮጵያ በምስራቅ አፍሪካ በርካታ ስደተኞችን ከሚያስተናግዱ ግንባር ቀደም ሀገራት አንዷ ስትሆን÷ የኤርትራ ስደተኞች ከደቡብ ሱዳንና ከሶማሊያ ቀጥሎ ሦስተኛውን ትልቅ ስብስብ ይይዛሉ።
የኢትዮጵያና የኤርትራ ህዝብ ተመሳሳይ የስነ ልቦና ውቅር፣ ታሪክ፣ ባህልና ኃይማኖት የሚጋሩ ህዝቦች በመሆናቸው፣ ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት ከ400 ሺህ በላይ የኤርትራ ስደተኞችን አስጠልላ ትገኛለች፡፡
ይህ ኢትዮጵያ ለጎረቤት ሀገራት ዜጎች የምታደርገውን ሰብዓዊ መስተንግዶ የሚያሳይ ሲሆን÷ ኤርትራውያንን ጨምሮ ኢትዮጵያ በአጠቃላይ የ1 ነጥብ 3 ሚሊየን ስደተኞች መጠለያ ናት፡፡
በአጠቃላይ ሻዕቢያ ኤርትራን ወደ ተሻለ የዴሞክራሲና የብልጽግና ምዕራፍ ማሸጋገር አልቻለም። ሻዕቢያ እነዚህን ቀውሶች ከራሱ የፖሊሲ ስህተት ይልቅ ከውጭ ሀገራት ጫና፣ ከድንበር አለመወሰንና ከዓለም አቀፍ ማዕቀቦች ጋር ለማያያዝ ይሞክራል፡፡
በሀገር ውስጥ ያለው ነባራዊ ሁኔታ ግን የሕዝቡን ህይወት እጅግ ፈታኝ አድርጎታል።
ኤርትራ ካለችበት ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ቀውስ እንድትወጣ፣ የአንድ ፓርቲ አገዛዝን ወደ ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓት መመለስ፣ የዜጎችን ሰብዓዊ መብቶች ማስከበርና የኢኮኖሚ ማሻሻያዎችን መተግበር የግድ ይላል።
9 days ago
የኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ ምላሽና ቀጣናዊ ፋይዳው
ኢትዮጵያ በአፍሪካ ቀንድ ባለፉት አስርት ዓመታት በሰላም ማስከበር፣ በግጭት አፈታት፣ በኤሌክትሪክ ኃይል ወጪ ንግድ፣ በቀጣናዊ ትስስር እና በንግድ ትብብር ረገድ ያበረከተችው አስተዋጽኦ ለጎረቤቶቿ ብሎም ለቀጣናው የምትሰጠውን ከፍ ያለ ትኩረት ያሳያል።
ኢትዮጵያ በታሪኳ የትኛውንም ጎረቤት ሀገር ወርራ አታውቅም፡፡ ከጎረቤቶቿ ጋር ያላት ግንኙነት ሰላማዊና በትብብር ላይ የተመሰረተ ሆኖ ቆይቷል፡፡
ጎረቤቶቿ ሰላም በራቃቸው ጊዜ ሁሉ፣ ሰላም ለማስከበር ቀድማ በመገኘት ትታወቃለች፡፡ ይህንንም በደቡብ ሱዳን፣ በሱዳን፣ በሶማሊያ እንዲሁም ከጎረቤቶቿ ራቅ ብላም በላይቤሪያ፣ በሩዋንዳ፣ በኮንጎ እና በሴራሊዮን በተግባር አስመስክራለች፡፡
በአህጉር ደረጃ ኢትዮጵያ በቅኝ ግዛት ቀንበር ሲማቅቁ የነበሩ አፍሪካውያን ወንድም እህቶች ነጻ ለመውጣት የሚያደርጉትን ጥረት በስልጠና፣ በሎጂስቲክስና በዲፕሎማሲ መስክ ጭምር መደገፏ አሌ የማይባል ሃቅ ነው፡፡
ኢትዮጵያ ዛሬም የልማት ትሩፋቷን ለብቻዋ ዕድገትና ለውጥ የምትጠቀም ሀገር አይደለችም፡፡ ይልቁንም ልማቷን እና ለውጧን በማጋራት እና ለጎረቤቶቿ አብሮ መለወጥ እየሰራች ትገኛለች፡፡
በአፍሪካ ከፍተኛ የኤሌክትሪክ ኃይል አምራች ከሆኑ ሀገራት መካከል አንዷ የሆነችው ኢትዮጵያ፤ ለጅቡቲ፣ ኬንያ፣ ሱዳን እና ደቡብ ሱዳን ኤሌክትሪክ እየላከች ነው።
ይህ በአካባቢው የኢንዱስትሪ ልማት፣ የከተማ እድገት እና የህዝብ ኑሮ መሻሻል ላይ ቀጥተኛ አስተዋፅኦ እያደረገ ነው።
በንግድ ረገድም ኢትዮጵያ የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና እና የአፍሪካ ህብረት "አጀንዳ 2063" የሚያስቀምጧቸውን የክልላዊ ውህደት ግቦች ለማሳካት የኢንዱስትሪ ፓርኮች፣ ልዩ የኢኮኖሚ ዞኖች፣ የድንበር ንግድ ማዕከላት እና የትራንስፖርት ኮሪደሮችን በማስፋፋት በቀጣናዊ ትስስር ማደግና መጠናከር ላይ ግዙፍ ኢንቨስትመንት እያካሄደች ነው።
ኢትዮጵያ ለጎረቤቶቿ ሰላምና ደህንነት፣ እድገትና ልማት አበክራ የሰራቻቸው ስራዎች ለቀጣናውና ለሀገራቱ ያላትን አዎንታዊ ሚና በግልፅ ያሳያል። ሀገሪቱ የባህር በር ጥያቄዋ ምላሽ ሲያገኝ ይህ ቀጣናዊ ገንቢ ሚናዋ በምን ያህል መጠን ሊያድግና ሊባዛ እንደሚችል ለመገመት አያዳግትም፡፡
በታሪክ አጋጣሚ የኢትዮጵያ ህዝብ ህጋዊ ስልጣን በሌለው አካል ህጋዊ የባሕር በር ባለቤትነቷን እንድታጣ ተደርጓል፡፡ የመደመር መንግሥት የተፈጸመውን ኢፍትሃዊና ታሪካዊ በደል በሰላማዊና ዲፕሎማሲያዊ መንገድ የማስመለስ ጥያቄ አቅርቦ የበርካታ ሃያላን ሀገራትን ድጋፍ አግኝቷል፡፡ ኢትዮጵያ በፍጥነት እያደገ ካለው ኢኮኖሚዋና የህዝብ ቁጥሯ አንጻር የባሕር በር አማራጭ ሊኖራት ይገባል።
በ60 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የባሕር በር እያለ ኢትዮጵያ ተዘግታ ትኑር የሚል ኢፍትሐዊነት ተቀባይነት የለውም።
የባሕር በር ጉዳይ ለኢትዮጵያ የንግድ መውጫ መግቢያ ብቻ ሳይሆን፤ የኢኮኖሚ ዕድገት፣ የብሔራዊ ደህንነት እና የጂኦፖለቲካ ስትራቴጂ ቁልፍ ጥያቄ በመሆኑ ጥያቄዋ መልስ እስኪያገኝ አበክራ ትሰራለች፡፡
ኢትዮጵያ የባህር በር ማግኘቷ ጥቅሙ ለእርሷ ብቻ አይደለም። በአፍሪካ ቀንድ እና በጎረቤት ሀገራት ዘንድ ከፍ ያለ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ የመፍጠር ሚና ይኖረዋል፡፡
በአካባቢው የንግድ ኮሪደሮች ስለሚፈጠሩ የወደብ አገልግሎት እንዲስፋፋ፣ የተለያዩ የመሰረተ ልማት አውታሮች እንዲገነቡ በማድረግ የንግድ ትስስርና አዳዲስ የስራ ዕድሎች ለመፍጠር ያስችላል።
በተጨማሪም ኢትዮጵያ ከታዳሽ ኃይል የምታመነጨው ኤሌክትሪክ ለቀጣናው በበቂ ሁኔታ ማቅረቧ ኢንዱስትሪዎችን ለማስፋፋትና የካርቦን ልቀትን ለመቀነስ ይረዳል።
ከዚህ ባሻገር የቀጣናዊ ሰላምና ጸጥታን በተመለከተ የጋራ ኢኮኖሚያዊ ጥቅም እያደገ ሲመጣ በሀገራት መካከል ከግጭት ይልቅ ትብብር እንዲጨምር ያደርጋል። ሀገራት በንግድ፣ በኢንቨስትመንት እና በመሠረተ ልማት በተጠናከረ ሁኔታ ሲተሳሰሩ ሰላምን የመጠበቅ ፍላጎታቸውም በዛው ልክ ይጨምራል።
የኢትዮጵያ የባሕር በር ጥያቄ ምላሽ ማግኘት የአፍሪካ ህብረት "አጀንዳ 2063" የሚጠይቀውን ቀጣናዊ ትስስር ለማጠናከር፣ የነፃ ንግድ ቀጣና ለመመስረት እና የመሠረተ ልማት ትስስርን ለማሳካት ጠንካራ መሠረት ለመጣል ያግዛል።
በመሆኑም የኢትዮጵያን የባሕር በር ጥያቄ አፋጣኝ መልስ እንዲያገኝ ለማድረግ ሀገራት፣ ዓለም አቀፍ፣ አህጉራዊ እና ቀጣናዊ ተቋማት ድጋፋቸውን ሊያጠናክሩ ይገባል፡፡
በቴዎድሮስ ሳህለ
ኢትዮጵያ በአፍሪካ ቀንድ ባለፉት አስርት ዓመታት በሰላም ማስከበር፣ በግጭት አፈታት፣ በኤሌክትሪክ ኃይል ወጪ ንግድ፣ በቀጣናዊ ትስስር እና በንግድ ትብብር ረገድ ያበረከተችው አስተዋጽኦ ለጎረቤቶቿ ብሎም ለቀጣናው የምትሰጠውን ከፍ ያለ ትኩረት ያሳያል።
ኢትዮጵያ በታሪኳ የትኛውንም ጎረቤት ሀገር ወርራ አታውቅም፡፡ ከጎረቤቶቿ ጋር ያላት ግንኙነት ሰላማዊና በትብብር ላይ የተመሰረተ ሆኖ ቆይቷል፡፡
ጎረቤቶቿ ሰላም በራቃቸው ጊዜ ሁሉ፣ ሰላም ለማስከበር ቀድማ በመገኘት ትታወቃለች፡፡ ይህንንም በደቡብ ሱዳን፣ በሱዳን፣ በሶማሊያ እንዲሁም ከጎረቤቶቿ ራቅ ብላም በላይቤሪያ፣ በሩዋንዳ፣ በኮንጎ እና በሴራሊዮን በተግባር አስመስክራለች፡፡
በአህጉር ደረጃ ኢትዮጵያ በቅኝ ግዛት ቀንበር ሲማቅቁ የነበሩ አፍሪካውያን ወንድም እህቶች ነጻ ለመውጣት የሚያደርጉትን ጥረት በስልጠና፣ በሎጂስቲክስና በዲፕሎማሲ መስክ ጭምር መደገፏ አሌ የማይባል ሃቅ ነው፡፡
ኢትዮጵያ ዛሬም የልማት ትሩፋቷን ለብቻዋ ዕድገትና ለውጥ የምትጠቀም ሀገር አይደለችም፡፡ ይልቁንም ልማቷን እና ለውጧን በማጋራት እና ለጎረቤቶቿ አብሮ መለወጥ እየሰራች ትገኛለች፡፡
በአፍሪካ ከፍተኛ የኤሌክትሪክ ኃይል አምራች ከሆኑ ሀገራት መካከል አንዷ የሆነችው ኢትዮጵያ፤ ለጅቡቲ፣ ኬንያ፣ ሱዳን እና ደቡብ ሱዳን ኤሌክትሪክ እየላከች ነው።
ይህ በአካባቢው የኢንዱስትሪ ልማት፣ የከተማ እድገት እና የህዝብ ኑሮ መሻሻል ላይ ቀጥተኛ አስተዋፅኦ እያደረገ ነው።
በንግድ ረገድም ኢትዮጵያ የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና እና የአፍሪካ ህብረት "አጀንዳ 2063" የሚያስቀምጧቸውን የክልላዊ ውህደት ግቦች ለማሳካት የኢንዱስትሪ ፓርኮች፣ ልዩ የኢኮኖሚ ዞኖች፣ የድንበር ንግድ ማዕከላት እና የትራንስፖርት ኮሪደሮችን በማስፋፋት በቀጣናዊ ትስስር ማደግና መጠናከር ላይ ግዙፍ ኢንቨስትመንት እያካሄደች ነው።
ኢትዮጵያ ለጎረቤቶቿ ሰላምና ደህንነት፣ እድገትና ልማት አበክራ የሰራቻቸው ስራዎች ለቀጣናውና ለሀገራቱ ያላትን አዎንታዊ ሚና በግልፅ ያሳያል። ሀገሪቱ የባህር በር ጥያቄዋ ምላሽ ሲያገኝ ይህ ቀጣናዊ ገንቢ ሚናዋ በምን ያህል መጠን ሊያድግና ሊባዛ እንደሚችል ለመገመት አያዳግትም፡፡
በታሪክ አጋጣሚ የኢትዮጵያ ህዝብ ህጋዊ ስልጣን በሌለው አካል ህጋዊ የባሕር በር ባለቤትነቷን እንድታጣ ተደርጓል፡፡ የመደመር መንግሥት የተፈጸመውን ኢፍትሃዊና ታሪካዊ በደል በሰላማዊና ዲፕሎማሲያዊ መንገድ የማስመለስ ጥያቄ አቅርቦ የበርካታ ሃያላን ሀገራትን ድጋፍ አግኝቷል፡፡ ኢትዮጵያ በፍጥነት እያደገ ካለው ኢኮኖሚዋና የህዝብ ቁጥሯ አንጻር የባሕር በር አማራጭ ሊኖራት ይገባል።
በ60 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የባሕር በር እያለ ኢትዮጵያ ተዘግታ ትኑር የሚል ኢፍትሐዊነት ተቀባይነት የለውም።
የባሕር በር ጉዳይ ለኢትዮጵያ የንግድ መውጫ መግቢያ ብቻ ሳይሆን፤ የኢኮኖሚ ዕድገት፣ የብሔራዊ ደህንነት እና የጂኦፖለቲካ ስትራቴጂ ቁልፍ ጥያቄ በመሆኑ ጥያቄዋ መልስ እስኪያገኝ አበክራ ትሰራለች፡፡
ኢትዮጵያ የባህር በር ማግኘቷ ጥቅሙ ለእርሷ ብቻ አይደለም። በአፍሪካ ቀንድ እና በጎረቤት ሀገራት ዘንድ ከፍ ያለ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ የመፍጠር ሚና ይኖረዋል፡፡
በአካባቢው የንግድ ኮሪደሮች ስለሚፈጠሩ የወደብ አገልግሎት እንዲስፋፋ፣ የተለያዩ የመሰረተ ልማት አውታሮች እንዲገነቡ በማድረግ የንግድ ትስስርና አዳዲስ የስራ ዕድሎች ለመፍጠር ያስችላል።
በተጨማሪም ኢትዮጵያ ከታዳሽ ኃይል የምታመነጨው ኤሌክትሪክ ለቀጣናው በበቂ ሁኔታ ማቅረቧ ኢንዱስትሪዎችን ለማስፋፋትና የካርቦን ልቀትን ለመቀነስ ይረዳል።
ከዚህ ባሻገር የቀጣናዊ ሰላምና ጸጥታን በተመለከተ የጋራ ኢኮኖሚያዊ ጥቅም እያደገ ሲመጣ በሀገራት መካከል ከግጭት ይልቅ ትብብር እንዲጨምር ያደርጋል። ሀገራት በንግድ፣ በኢንቨስትመንት እና በመሠረተ ልማት በተጠናከረ ሁኔታ ሲተሳሰሩ ሰላምን የመጠበቅ ፍላጎታቸውም በዛው ልክ ይጨምራል።
የኢትዮጵያ የባሕር በር ጥያቄ ምላሽ ማግኘት የአፍሪካ ህብረት "አጀንዳ 2063" የሚጠይቀውን ቀጣናዊ ትስስር ለማጠናከር፣ የነፃ ንግድ ቀጣና ለመመስረት እና የመሠረተ ልማት ትስስርን ለማሳካት ጠንካራ መሠረት ለመጣል ያግዛል።
በመሆኑም የኢትዮጵያን የባሕር በር ጥያቄ አፋጣኝ መልስ እንዲያገኝ ለማድረግ ሀገራት፣ ዓለም አቀፍ፣ አህጉራዊ እና ቀጣናዊ ተቋማት ድጋፋቸውን ሊያጠናክሩ ይገባል፡፡
በቴዎድሮስ ሳህለ
11 days ago
የታዳሽ ኃይል ልማት ጉዞዋን ያጠናከረችው ኢትዮጵያ
የኢትዮጵያ ታዳሽ ኃይል ልማትና የቀጣናው ትስስር ጉዞ እየተሻሻለ እና ወደ አስተማማኝ አጋርነት እያደገ ይገኛል፡፡
ለአንድ ሀገር የኢኮኖሚ ዕድገትና የኢንዱስትሪ ሽግግር እንዲሁም ሁለንተናዊ ብልጽግና አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት ወሳኝ ነው፡፡
ኢትዮጵያ ይህንን እውነት በመረዳት በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ መሪነት የሀገሪቱን የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት የሚያሰፉና የሚያዘምኑ ዘርፈ ብዙ ሥራዎችን በስፋት እያከናወነች ትገኛለች።
ይህ ስትራቴጂካዊ ጉዞ በሚሊየን የሚቆጠሩ ዜጎችን ከጨለማ ከማውጣት ባለፈ ሀገሪቱን የምሥራቅ አፍሪካ የኃይል ማዕከል ለማድረግ ያለመ ታላቅ ብሔራዊ ራዕይ ነው።
የዚህ ግዙፍ የኃይል መሠረተ ልማት ግንባታ ግንባር ቀደም ተምሳሌት የሆነው የሕዳሴ ግድብ የኢትዮጵያውያን የጽናት፣ የጥበብ፣ የአብሮነትና የመተባበር መገለጫ ነው።
ግድቡ የዓባይን ወንዝ ተፈጥሯዊ ፍሰት ሳይገታና የታችኛውን ተፋሰስ ሀገራት ጥቅም ሳይነካ የውሃውን ኃይል ወደ ንጹህ የኤሌክትሪክ ብርሃንነት በመቀየር ረገድ ታሪካዊ ምዕራፍ እየፈጠረ ይገኛል።
የውሃ አሞላልና የግንባታ ምዕራፎቹን በተሳካ ሁኔታ እያጠናቀቀ የሚገኘው ይህ ግዙፍ ተቋም፣ የሀገሪቱን የኤሌክትሪክ አቅርቦት በእጥፍ ለማሳደግ ታላቅ አቅም ሆኗል።
ግድቡ ለኢንዱስትሪ ፓርኮች፣ ለከተሞች መስፋፋትና ለገጠር አካባቢዎች የብርሃን ምንጭ በመሆን የኢኮኖሚውን ሞተር በማንቀሳቀስ ላይ ነው።
ነገር ግን የኢትዮጵያ የኃይል ስትራቴጂ በውሃ ሀይል ወይም በሕዳሴው ግድብ ላይ ብቻ የተገደበ አይደለም።ሀገሪቱ የኃይል ምንጮቿን ከማስፋት ረገድ ዘርፈ ብዙ ሥራዎችን እያከናወነች ትገኛለች።
በውሃ ኃይል ረገድ እንደ ኮይሻ፣ ግልገል ጊቤ እና ሌሎች የወንዝ ተፋሰሶች ላይ የተገነቡና በመገንባት ላይ ያሉ ግዙፍ ፕሮጀክቶች ተጨማሪ በሺዎች የሚቆጠሩ ሜጋ ዋት ሀይልን ለብሔራዊ ኃይል ቋት እያበረከቱ ናቸው።
ከዚህም በተጓዳኝ፣ ኢትዮጵያ ካላት የተፈጥሮ ጸጋ በመነሳት የንፋስ ኃይል፣ የፀሐይ ብርሃን ኃይል እና የምድር ውስጥ እንፋሎት ልማቶችን በስፋት እያከናወነች ትገኛለች።
እንደ አሸጎዳ እና አዳማ ያሉ የንፋስ ኃይል ማመንጫዎች እንዲሁም የአሉቶ ላንጋኖ የምድር ውስጥ እንፋሎት ፕሮጀክቶች የሀገሪቱን ታዳሽ ኃይል ይበልጥ አስተማማኝ እና ከተፈጥሮ መዛባት የተጠበቀ እያደረጉት ይገኛሉ።
ይህ በሀገር ውስጥ የሚመነጨው ግዙፍ የኃይል አቅም ከኢትዮጵያ ድንበር አልፎ ቀጣናዊ ትስስርን ለመፍጠር ትልቅ መሣሪያ እየሆነ ነው።
ኢትዮጵያ "የምሥራቅ አፍሪካ የኃይል ማማ" የመሆን ራዕይዋን ለማሳካት የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመሮችን በመዘርጋት ላይ ትገኛለች።
በአሁኑ ወቅት ለጎረቤት ሀገራት እንደ ኬንያ፣ ሱዳን፣ ደቡብ ሱዳን እና ጅቡቲ የኤሌክትሪክ ኃይል በማቅረብ ላይ የምትገኝ ሲሆን÷ ይህ ትስስር ወደ ታንዛኒያ እና ሌሎች የደቡብ አፍሪካ ቀጣና ሀገራት እንዲደርስ ሰፊ የዲፕሎማሲና የቴክኒክ ስራዎች እየተሰሩ ይገኛሉ፤ የሙከራ ሸያጭ የተጀመረባቸው ሀገራትም አሉ።
ይህ የኃይል ሽያጭ ለሀገሪቱ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ የሚያስገኝ ከመሆኑም በላይ በቀጣናው ሀገራት መካከል ያለውን የሰላምና የኢኮኖሚ ትስስር ይበልጥ ማጠናከሪያ የዲፕሎማሲ መሳሪያ ሆኖ ያገለግላል።
ኢትዮጵያ በሕዳሴው ግድብና በሌሎች ዘርፈ ብዙ የታዳሽ ኃይል ፕሮጀክቶች ላይ እያደረገችው ያለው ርብርብ የሀገር ውስጥ የኤሌክትሪክ ፍላጎትን ለማሟላት ብቻ ሳይሆን ለአካባቢ ጥበቃና ለአረንጓዴ ኢኮኖሚ ዕድገት ያላትን ቁርጠኝነት የሚያሳይ ማረጋገጫ ነው።
ኢትዮጵያ በተጠናቀቀው 2018 በጀት ዓመት ከተለያዩ የሃይል ምንጮች 9 ሺህ 730 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ሃይል አመንጭታለች፡፡
በእመቤት ሲሳይ
የኢትዮጵያ ታዳሽ ኃይል ልማትና የቀጣናው ትስስር ጉዞ እየተሻሻለ እና ወደ አስተማማኝ አጋርነት እያደገ ይገኛል፡፡
ለአንድ ሀገር የኢኮኖሚ ዕድገትና የኢንዱስትሪ ሽግግር እንዲሁም ሁለንተናዊ ብልጽግና አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት ወሳኝ ነው፡፡
ኢትዮጵያ ይህንን እውነት በመረዳት በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ መሪነት የሀገሪቱን የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት የሚያሰፉና የሚያዘምኑ ዘርፈ ብዙ ሥራዎችን በስፋት እያከናወነች ትገኛለች።
ይህ ስትራቴጂካዊ ጉዞ በሚሊየን የሚቆጠሩ ዜጎችን ከጨለማ ከማውጣት ባለፈ ሀገሪቱን የምሥራቅ አፍሪካ የኃይል ማዕከል ለማድረግ ያለመ ታላቅ ብሔራዊ ራዕይ ነው።
የዚህ ግዙፍ የኃይል መሠረተ ልማት ግንባታ ግንባር ቀደም ተምሳሌት የሆነው የሕዳሴ ግድብ የኢትዮጵያውያን የጽናት፣ የጥበብ፣ የአብሮነትና የመተባበር መገለጫ ነው።
ግድቡ የዓባይን ወንዝ ተፈጥሯዊ ፍሰት ሳይገታና የታችኛውን ተፋሰስ ሀገራት ጥቅም ሳይነካ የውሃውን ኃይል ወደ ንጹህ የኤሌክትሪክ ብርሃንነት በመቀየር ረገድ ታሪካዊ ምዕራፍ እየፈጠረ ይገኛል።
የውሃ አሞላልና የግንባታ ምዕራፎቹን በተሳካ ሁኔታ እያጠናቀቀ የሚገኘው ይህ ግዙፍ ተቋም፣ የሀገሪቱን የኤሌክትሪክ አቅርቦት በእጥፍ ለማሳደግ ታላቅ አቅም ሆኗል።
ግድቡ ለኢንዱስትሪ ፓርኮች፣ ለከተሞች መስፋፋትና ለገጠር አካባቢዎች የብርሃን ምንጭ በመሆን የኢኮኖሚውን ሞተር በማንቀሳቀስ ላይ ነው።
ነገር ግን የኢትዮጵያ የኃይል ስትራቴጂ በውሃ ሀይል ወይም በሕዳሴው ግድብ ላይ ብቻ የተገደበ አይደለም።ሀገሪቱ የኃይል ምንጮቿን ከማስፋት ረገድ ዘርፈ ብዙ ሥራዎችን እያከናወነች ትገኛለች።
በውሃ ኃይል ረገድ እንደ ኮይሻ፣ ግልገል ጊቤ እና ሌሎች የወንዝ ተፋሰሶች ላይ የተገነቡና በመገንባት ላይ ያሉ ግዙፍ ፕሮጀክቶች ተጨማሪ በሺዎች የሚቆጠሩ ሜጋ ዋት ሀይልን ለብሔራዊ ኃይል ቋት እያበረከቱ ናቸው።
ከዚህም በተጓዳኝ፣ ኢትዮጵያ ካላት የተፈጥሮ ጸጋ በመነሳት የንፋስ ኃይል፣ የፀሐይ ብርሃን ኃይል እና የምድር ውስጥ እንፋሎት ልማቶችን በስፋት እያከናወነች ትገኛለች።
እንደ አሸጎዳ እና አዳማ ያሉ የንፋስ ኃይል ማመንጫዎች እንዲሁም የአሉቶ ላንጋኖ የምድር ውስጥ እንፋሎት ፕሮጀክቶች የሀገሪቱን ታዳሽ ኃይል ይበልጥ አስተማማኝ እና ከተፈጥሮ መዛባት የተጠበቀ እያደረጉት ይገኛሉ።
ይህ በሀገር ውስጥ የሚመነጨው ግዙፍ የኃይል አቅም ከኢትዮጵያ ድንበር አልፎ ቀጣናዊ ትስስርን ለመፍጠር ትልቅ መሣሪያ እየሆነ ነው።
ኢትዮጵያ "የምሥራቅ አፍሪካ የኃይል ማማ" የመሆን ራዕይዋን ለማሳካት የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመሮችን በመዘርጋት ላይ ትገኛለች።
በአሁኑ ወቅት ለጎረቤት ሀገራት እንደ ኬንያ፣ ሱዳን፣ ደቡብ ሱዳን እና ጅቡቲ የኤሌክትሪክ ኃይል በማቅረብ ላይ የምትገኝ ሲሆን÷ ይህ ትስስር ወደ ታንዛኒያ እና ሌሎች የደቡብ አፍሪካ ቀጣና ሀገራት እንዲደርስ ሰፊ የዲፕሎማሲና የቴክኒክ ስራዎች እየተሰሩ ይገኛሉ፤ የሙከራ ሸያጭ የተጀመረባቸው ሀገራትም አሉ።
ይህ የኃይል ሽያጭ ለሀገሪቱ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ የሚያስገኝ ከመሆኑም በላይ በቀጣናው ሀገራት መካከል ያለውን የሰላምና የኢኮኖሚ ትስስር ይበልጥ ማጠናከሪያ የዲፕሎማሲ መሳሪያ ሆኖ ያገለግላል።
ኢትዮጵያ በሕዳሴው ግድብና በሌሎች ዘርፈ ብዙ የታዳሽ ኃይል ፕሮጀክቶች ላይ እያደረገችው ያለው ርብርብ የሀገር ውስጥ የኤሌክትሪክ ፍላጎትን ለማሟላት ብቻ ሳይሆን ለአካባቢ ጥበቃና ለአረንጓዴ ኢኮኖሚ ዕድገት ያላትን ቁርጠኝነት የሚያሳይ ማረጋገጫ ነው።
ኢትዮጵያ በተጠናቀቀው 2018 በጀት ዓመት ከተለያዩ የሃይል ምንጮች 9 ሺህ 730 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ሃይል አመንጭታለች፡፡
በእመቤት ሲሳይ
12 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የሱዳን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ማሂ ኤል-ዲን ሳሌም፣ አሜሪካ፣ ብሪታንያ እና የአውሮፓ ኅብረት በሀገራቸው ላይ የጣሉት ማዕቀብ ግቡን የማያሳካ "የፖለቲካ መሣሪያ" መሆኑን ገለጹ። ሚኒስትሩ በወቅታዊ የሱዳን ጉዳዮች ላይ በሰጡት ሰፊ መግለጫ፣ በሱዳን ጦርነት ውስጥ የውጭ ኃይሎች እጅ እንዳለበት በተጨባጭ መረጋገጡን እና ከጦርነቱ በኋላ የሀገሪቱ ዲፕሎማሲ የተለየ መልክ እንደሚኖረው አስታውቀዋል።
አምባሳደር ማሂ ኤል-ዲን እንዳብራሩት፣ በሱዳን ጉዳይ የውጭ ሀገራት ጣልቃ ገብነት መኖሩን የሚነሱት ጉዳዮች ክስ ሳይሆኑ በተጨባጭ መረጃ የተረጋገጡ እውነታዎች ናቸው። ለአብነትም በአሜሪካ የሚገኘው የዬል ዩኒቨርሲቲ የሳተላይት መረጃዎችን በመጠቀም እንደ ኢትዮጵያ ባለ ቀጣና ውስጥ የጦር ካምፖች መቋቋማቸውን ማረጋገጡን፣ እንዲሁም እንደ ዋሽንግተን ፖስት ያሉ ታላላቅ ዓለም አቀፍ ተቋማት ጉዳዩን መዘገባቸውን አስታውሰዋል። ሚኒስትሩ አክለውም ኃይሎቹ እና ቅጥረኛ ተዋጊዎች ከቻድ፣ ከምስራቃዊ ሊቢያ (በሀፍታር ቡድን በኩል)፣ አልፎ ተርፎም ከኮሎምቢያ ሳይቀር ድንበር አቋርጠው ወደ ካርቱም እየገቡ መሆናቸውን ገልጸዋል። በደቡብ ሱዳን በኩልም መንግሥት ቀጥተኛ ሚና ባይኖረውም፣ ሕገ-ወጦች እና አማፂያን በሌላ መንገድ ወደ ሱዳን እየገቡ መሆኑን ጠቁመዋል።
ምንም እንኳን አንዳንድ ጎረቤት ሀገራት ሚሊሺያዎችን እና ቅጥረኛ ተዋጊዎችን ቢያስተባብሩም፣ ሱዳን ግን ታሪክ ያላት፣ የጎለመሰች እና በመልካም ጉርብትና የምትታወቅ ሀገር በመሆኗ እስከ አሁን ድረስ ከእነዚህ ሀገራት የሚመጡ ስደተኞችን በክብር እያስተናገደች እንደምትገኝ አብራርተዋል። በሌላ በኩል፣ በሱዳን ላይ ለተቃጣው ፈተና ከጎናቸው ለቆሙት እንደ ኤርትራ እና ግብፅ ላሉ እህትማማች ሀገራት የላቀ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
ጦርነቱን ተከትሎ የሱዳን የውጭ ግንኙነት ፖሊሲ ላይ ትልቅ ለውጥ እንደሚደረግ ያረጋገጡት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ፣ ከጦርነቱ በኋላ የሱዳን ዲፕሎማሲ የተለየ መልክ እንደሚኖረው እና የሀገራትን አቋም በድጋሚ መገምገም ግድ እንደሚል ተናግረዋል። "ማነው ከእኛ ጋር የቆመው? ማነው ከዚህ ሚሊሺያ ጋር በመሆን በሱዳን ህዝብ ላይ የቆመው? የሚለውን ቅርብም ሆኑ ሩቅ ያሉ ሀገራትን አቋም መገምገም አለብን" ብለዋል።
የሱዳን ህዝብ በለጋስነቱና በመቻቻል የሚታወቅ፣ እንዲሁም በየትኛውም ሀገር ላይ ጥቃት ሰንዝሮ የማያውቅ ሰላማዊ ህዝብ መሆኑን በመጥቀስ፤ በአሁኑ ወቅት በማያሻማ መልኩ በህዝቡ ላይ የተከፈተበት ጦርነት ግን የሁሉንም ሱዳናዊ ህይወት፣ ዘመድ፣ ንብረት፣ ትምህርት እና የህክምና አገልግሎት ያመሰቃቀለ ዘግናኝ ጥቃት በመሆኑ፣ ከዚህ እውነታ አንፃር ሀገሪቱ የዲፕሎማሲ ግንኙነቷን እንደገና ማስተካከል እጅግ አስፈላጊ መሆኑን አስገንዝበዋል።
አምባሳደር ማሂ ኤል-ዲን እንዳብራሩት፣ በሱዳን ጉዳይ የውጭ ሀገራት ጣልቃ ገብነት መኖሩን የሚነሱት ጉዳዮች ክስ ሳይሆኑ በተጨባጭ መረጃ የተረጋገጡ እውነታዎች ናቸው። ለአብነትም በአሜሪካ የሚገኘው የዬል ዩኒቨርሲቲ የሳተላይት መረጃዎችን በመጠቀም እንደ ኢትዮጵያ ባለ ቀጣና ውስጥ የጦር ካምፖች መቋቋማቸውን ማረጋገጡን፣ እንዲሁም እንደ ዋሽንግተን ፖስት ያሉ ታላላቅ ዓለም አቀፍ ተቋማት ጉዳዩን መዘገባቸውን አስታውሰዋል። ሚኒስትሩ አክለውም ኃይሎቹ እና ቅጥረኛ ተዋጊዎች ከቻድ፣ ከምስራቃዊ ሊቢያ (በሀፍታር ቡድን በኩል)፣ አልፎ ተርፎም ከኮሎምቢያ ሳይቀር ድንበር አቋርጠው ወደ ካርቱም እየገቡ መሆናቸውን ገልጸዋል። በደቡብ ሱዳን በኩልም መንግሥት ቀጥተኛ ሚና ባይኖረውም፣ ሕገ-ወጦች እና አማፂያን በሌላ መንገድ ወደ ሱዳን እየገቡ መሆኑን ጠቁመዋል።
ምንም እንኳን አንዳንድ ጎረቤት ሀገራት ሚሊሺያዎችን እና ቅጥረኛ ተዋጊዎችን ቢያስተባብሩም፣ ሱዳን ግን ታሪክ ያላት፣ የጎለመሰች እና በመልካም ጉርብትና የምትታወቅ ሀገር በመሆኗ እስከ አሁን ድረስ ከእነዚህ ሀገራት የሚመጡ ስደተኞችን በክብር እያስተናገደች እንደምትገኝ አብራርተዋል። በሌላ በኩል፣ በሱዳን ላይ ለተቃጣው ፈተና ከጎናቸው ለቆሙት እንደ ኤርትራ እና ግብፅ ላሉ እህትማማች ሀገራት የላቀ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
ጦርነቱን ተከትሎ የሱዳን የውጭ ግንኙነት ፖሊሲ ላይ ትልቅ ለውጥ እንደሚደረግ ያረጋገጡት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ፣ ከጦርነቱ በኋላ የሱዳን ዲፕሎማሲ የተለየ መልክ እንደሚኖረው እና የሀገራትን አቋም በድጋሚ መገምገም ግድ እንደሚል ተናግረዋል። "ማነው ከእኛ ጋር የቆመው? ማነው ከዚህ ሚሊሺያ ጋር በመሆን በሱዳን ህዝብ ላይ የቆመው? የሚለውን ቅርብም ሆኑ ሩቅ ያሉ ሀገራትን አቋም መገምገም አለብን" ብለዋል።
የሱዳን ህዝብ በለጋስነቱና በመቻቻል የሚታወቅ፣ እንዲሁም በየትኛውም ሀገር ላይ ጥቃት ሰንዝሮ የማያውቅ ሰላማዊ ህዝብ መሆኑን በመጥቀስ፤ በአሁኑ ወቅት በማያሻማ መልኩ በህዝቡ ላይ የተከፈተበት ጦርነት ግን የሁሉንም ሱዳናዊ ህይወት፣ ዘመድ፣ ንብረት፣ ትምህርት እና የህክምና አገልግሎት ያመሰቃቀለ ዘግናኝ ጥቃት በመሆኑ፣ ከዚህ እውነታ አንፃር ሀገሪቱ የዲፕሎማሲ ግንኙነቷን እንደገና ማስተካከል እጅግ አስፈላጊ መሆኑን አስገንዝበዋል።
Sponsored by
Surafel
12 days ago
የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን ተቋማዊ ሪፎርም ተጠናክሮ ቀጥሏል
#ethiopia | የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን ሁለንተናዊ ሀገራዊ ለውጡን መነሻ በማድረግ ለበርካታ ዓመታት ሲተገብረው የቆየውን ተቋማዊ ሪፎርም በተጠናከረ ሁኔታ እንደሚቀጥል አስታውቋል። በ2019 በጀት ዓመትም ሪፎርሙን የበለጠ ለማጠናከር የሚያስችሉ ስትራቴጂካዊ አቅጣጫዎች ተቀምጠዋል።
ኮርፖሬሽኑ የ2018 በጀት ዓመት የሥራ አፈጻጸም ግምገማ እና የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ውይይትን በቢሾፍቱ ከተማ ለሁለት ቀናት ያካሄደ ሲሆን፣ በበጀት ዓመቱ የታቀዱ ሥራዎችን 97 በመቶ ማሳካቱ ተገልጿል። በገቢ ዕድገት፣ በቤት ልማት፣ በአፈጻጸም አቅም እና በቤት አስተዳደር የተመዘገቡ ውጤቶችም የተቋሙን የለውጥ ጉዞ እንዳጠናከሩ ተጠቁሟል።
በተጨማሪም የሕዝብና የመንግሥት ጥቅምን ለማስጠበቅ በተደረጉ የፍርድ ቤት ክርክሮች በርካታ ይዞታዎችን ማስመለስ መቻሉ ተገልጿል።
በውጭ ገበያ መስፋፋትን በተመለከተም፣ በደቡብ ሱዳን ጁባ ከተማ የቤት ልማት ፕሮጀክት ለማከናወን ከደቡብ ሱዳን ኢኳቶሪያል ስቴት ጋር የተደረሰውን ስምምነት ወደ ተግባር ለማስገባት ሥራዎች በመካሄድ ላይ እንደሚገኙ ተገልጿል።
በፕሮጀክቶች ዘርፍ የፒያሳ እና የጎልድ ሳይት ፕሮጀክቶች ተጠናቀው ወደ አገልግሎት መግባታቸው የተጠቀሰ ሲሆን፣ ዘመናዊ 3ዲ የግንባታ ቴክኖሎጂን ለማስፋፋት የመጀመሪያ የሙከራ ቤቶች ግንባታም በሂደት ላይ መሆኑ ተገልጿል።
በተጨማሪም የቤቶች ቆጠራና የመረጃ ማሰባሰብ ሥራ በመጠናቀቁ ዘመናዊ የቤት አስተዳደር ሥርዓት መጠናከሩን እና ከደንበኞች ጋር በትብብር የተገነቡ የንግድ ቤቶች ወደ ኪራይ አገልግሎት በመግባታቸው ከፍተኛ ገቢ ማስገኘት መጀመራቸው ተጠቁሟል።
ኮርፖሬሽኑ በ50ኛ ዓመት ኢዮቤልዩ በዓሉ ወቅት የተቋሙን የግማሽ ምዕተ ዓመት ታሪክና ስኬቶች የሚያሳዩ መርሃ ግብሮችን ለአራት ተከታታይ ቀናት በድምቀት ማካሄዱ ተገልጿል። ይህም የተቋሙን ገጽታ በአዎንታዊ መልኩ ለመቀየር አስተዋጽኦ እንዳደረገ ተጠቅሷል።
በ2019 በጀት ዓመት የሚተገበሩ ዋና ዋና የትኩረት አቅጣጫዎች ዘመናዊና ፈጣን የግንባታ ቴክኖሎጂዎችን በስፋት ሥራ ላይ ማዋል፣ የቤት አቅርቦትን ለማሳደግ ሰፋፊ የቤት ልማት ፕሮግራሞችን መተግበር፣ የገቢ ምንጮችንና የፋይናንስ አማራጮችን ማስፋፋት እንዲሁም የሰው ኃይልና የአሠራር አቅምን ማጠናከር መሆናቸው ተገልጿል።
ኮርፖሬሽኑም እነዚህን ስትራቴጂያዊ አቅጣጫዎች በመተግበር ለሀገራዊ የቤት ልማት ዕቅድ ስኬት በቁርጠኝነት እንደሚሰራ አስታውቋል።
#ethiopia | የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን ሁለንተናዊ ሀገራዊ ለውጡን መነሻ በማድረግ ለበርካታ ዓመታት ሲተገብረው የቆየውን ተቋማዊ ሪፎርም በተጠናከረ ሁኔታ እንደሚቀጥል አስታውቋል። በ2019 በጀት ዓመትም ሪፎርሙን የበለጠ ለማጠናከር የሚያስችሉ ስትራቴጂካዊ አቅጣጫዎች ተቀምጠዋል።
ኮርፖሬሽኑ የ2018 በጀት ዓመት የሥራ አፈጻጸም ግምገማ እና የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ውይይትን በቢሾፍቱ ከተማ ለሁለት ቀናት ያካሄደ ሲሆን፣ በበጀት ዓመቱ የታቀዱ ሥራዎችን 97 በመቶ ማሳካቱ ተገልጿል። በገቢ ዕድገት፣ በቤት ልማት፣ በአፈጻጸም አቅም እና በቤት አስተዳደር የተመዘገቡ ውጤቶችም የተቋሙን የለውጥ ጉዞ እንዳጠናከሩ ተጠቁሟል።
በተጨማሪም የሕዝብና የመንግሥት ጥቅምን ለማስጠበቅ በተደረጉ የፍርድ ቤት ክርክሮች በርካታ ይዞታዎችን ማስመለስ መቻሉ ተገልጿል።
በውጭ ገበያ መስፋፋትን በተመለከተም፣ በደቡብ ሱዳን ጁባ ከተማ የቤት ልማት ፕሮጀክት ለማከናወን ከደቡብ ሱዳን ኢኳቶሪያል ስቴት ጋር የተደረሰውን ስምምነት ወደ ተግባር ለማስገባት ሥራዎች በመካሄድ ላይ እንደሚገኙ ተገልጿል።
በፕሮጀክቶች ዘርፍ የፒያሳ እና የጎልድ ሳይት ፕሮጀክቶች ተጠናቀው ወደ አገልግሎት መግባታቸው የተጠቀሰ ሲሆን፣ ዘመናዊ 3ዲ የግንባታ ቴክኖሎጂን ለማስፋፋት የመጀመሪያ የሙከራ ቤቶች ግንባታም በሂደት ላይ መሆኑ ተገልጿል።
በተጨማሪም የቤቶች ቆጠራና የመረጃ ማሰባሰብ ሥራ በመጠናቀቁ ዘመናዊ የቤት አስተዳደር ሥርዓት መጠናከሩን እና ከደንበኞች ጋር በትብብር የተገነቡ የንግድ ቤቶች ወደ ኪራይ አገልግሎት በመግባታቸው ከፍተኛ ገቢ ማስገኘት መጀመራቸው ተጠቁሟል።
ኮርፖሬሽኑ በ50ኛ ዓመት ኢዮቤልዩ በዓሉ ወቅት የተቋሙን የግማሽ ምዕተ ዓመት ታሪክና ስኬቶች የሚያሳዩ መርሃ ግብሮችን ለአራት ተከታታይ ቀናት በድምቀት ማካሄዱ ተገልጿል። ይህም የተቋሙን ገጽታ በአዎንታዊ መልኩ ለመቀየር አስተዋጽኦ እንዳደረገ ተጠቅሷል።
በ2019 በጀት ዓመት የሚተገበሩ ዋና ዋና የትኩረት አቅጣጫዎች ዘመናዊና ፈጣን የግንባታ ቴክኖሎጂዎችን በስፋት ሥራ ላይ ማዋል፣ የቤት አቅርቦትን ለማሳደግ ሰፋፊ የቤት ልማት ፕሮግራሞችን መተግበር፣ የገቢ ምንጮችንና የፋይናንስ አማራጮችን ማስፋፋት እንዲሁም የሰው ኃይልና የአሠራር አቅምን ማጠናከር መሆናቸው ተገልጿል።
ኮርፖሬሽኑም እነዚህን ስትራቴጂያዊ አቅጣጫዎች በመተግበር ለሀገራዊ የቤት ልማት ዕቅድ ስኬት በቁርጠኝነት እንደሚሰራ አስታውቋል።
17 days ago
አሜሪካ ወደ በርካታ የአፍሪካ ሀገራት የ«አትሂዱ» ጥብቅ መመሪያ አስተላለፈች
የዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የዓለም ሀገራትን የፀጥታ ሁኔታ መነሻ በማድረግ በሚያወጣው መመሪያ፣ በርካታ የአፍሪካ ሀገራትን በከፍተኛው የደረጃ 4 የጉዞ ማስጠንቀቂያ ዝርዝር ውስጥ አስፍሯል።
ዋሽንግተን የራሷ ዜጎች ወደነዚህ ሀገራት ፍጹም ጉዞ እንዳያደርጉ ያሳሰበችው በእነዚህ ቀጠናዎች ባለው እጅግ አሳሳቢ የፀጥታ ችግር፣ የሽብርተኝነት ስጋት፣ የእርስ በርስ ግጭቶች፣ የታጠቁ አማፂያን ጥቃት እና ለአሜሪካ ዜጎች የሚሰጠው የቆንስላ ወይም የድንገተኛ ጊዜ ድጋፍ እጅግ ውስን በመሆኑ ነው።
በዚህ የዩናይትድ ስቴትስ የ«አትሂዱ» ጥብቅ መመሪያ ውስጥ ከተካተቱት የአፍሪካ ሀገራት መካከል ቡርኪና ፋሶ፣ ሊቢያ፣ ማሊ፣ ኒጀር፣ ሶማሊያ፣ ደቡብ ሱዳን፣ ሱዳንና ማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ በዋናነት የሚጠቀሱ ሲሆን፣ እንደ ቻድ እና ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ያሉ ሀገራት ደግሞ በተለይ ከጎረቤት ሀገራት ጋር በሚያገናኟቸው ድንበሮችና የተወሰኑ ከፍተኛ ስጋት ያለባቸው ግዛቶቻቸው ላይ ተመሳሳይ የደረጃ 4 እገዳ ተጥሎባቸዋል።
በሌላ በኩል ዩጋንዳ በደረጃ 3 (Reconsider Travel ወይም ጉዞን መልሶ ማሰብ) ስር የምትገኝ ሲሆን፣ ዜጎች ወደ ሀገሪቱ ከመጓዛቸው በፊት በወንጀል እና በሽብርተኝነት ስጋቶች ዙሪያ ከፍተኛ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ ተመክሯል።
ይህ በአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በየጊዜው የሚሻሻለው የደረጃ 4 የጉዞ ማስጠንቀቂያ ከአፍሪካ ውጭ እንደ ሩሲያ፣ ዩክሬን፣ አፍጋኒስታን፣ ሰሜን ኮሪያ፣ የመን፣ ሶሪያ፣ ቬንዙዌላ፣ ኢራን እና ጋዛን ጨምሮ ሌሎች ከፍተኛ የጦርነትና የፖለቲካ ቀውስ ውስጥ ያሉ የዓለማችን አካባቢዎችንም ያጠቃልላል።
Seledadotio
Seledadotio
የዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የዓለም ሀገራትን የፀጥታ ሁኔታ መነሻ በማድረግ በሚያወጣው መመሪያ፣ በርካታ የአፍሪካ ሀገራትን በከፍተኛው የደረጃ 4 የጉዞ ማስጠንቀቂያ ዝርዝር ውስጥ አስፍሯል።
ዋሽንግተን የራሷ ዜጎች ወደነዚህ ሀገራት ፍጹም ጉዞ እንዳያደርጉ ያሳሰበችው በእነዚህ ቀጠናዎች ባለው እጅግ አሳሳቢ የፀጥታ ችግር፣ የሽብርተኝነት ስጋት፣ የእርስ በርስ ግጭቶች፣ የታጠቁ አማፂያን ጥቃት እና ለአሜሪካ ዜጎች የሚሰጠው የቆንስላ ወይም የድንገተኛ ጊዜ ድጋፍ እጅግ ውስን በመሆኑ ነው።
በዚህ የዩናይትድ ስቴትስ የ«አትሂዱ» ጥብቅ መመሪያ ውስጥ ከተካተቱት የአፍሪካ ሀገራት መካከል ቡርኪና ፋሶ፣ ሊቢያ፣ ማሊ፣ ኒጀር፣ ሶማሊያ፣ ደቡብ ሱዳን፣ ሱዳንና ማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ በዋናነት የሚጠቀሱ ሲሆን፣ እንደ ቻድ እና ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ያሉ ሀገራት ደግሞ በተለይ ከጎረቤት ሀገራት ጋር በሚያገናኟቸው ድንበሮችና የተወሰኑ ከፍተኛ ስጋት ያለባቸው ግዛቶቻቸው ላይ ተመሳሳይ የደረጃ 4 እገዳ ተጥሎባቸዋል።
በሌላ በኩል ዩጋንዳ በደረጃ 3 (Reconsider Travel ወይም ጉዞን መልሶ ማሰብ) ስር የምትገኝ ሲሆን፣ ዜጎች ወደ ሀገሪቱ ከመጓዛቸው በፊት በወንጀል እና በሽብርተኝነት ስጋቶች ዙሪያ ከፍተኛ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ ተመክሯል።
ይህ በአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በየጊዜው የሚሻሻለው የደረጃ 4 የጉዞ ማስጠንቀቂያ ከአፍሪካ ውጭ እንደ ሩሲያ፣ ዩክሬን፣ አፍጋኒስታን፣ ሰሜን ኮሪያ፣ የመን፣ ሶሪያ፣ ቬንዙዌላ፣ ኢራን እና ጋዛን ጨምሮ ሌሎች ከፍተኛ የጦርነትና የፖለቲካ ቀውስ ውስጥ ያሉ የዓለማችን አካባቢዎችንም ያጠቃልላል።
Seledadotio
Seledadotio
17 days ago
ተስፋን በምድራችን፦ የ50 ቢሊዮን ችግኝ ራዕይ
**********************
(የዕለቱ መልዕከት)
የዘንድሮው ክረምት የሀገራችንን የ50 ቢሊዮን ችግኞች ተከላ ግዙፍ ራዕይ ሙሉ በሙሉ እውን በማድረግ የምናጠናቅቅበት ታሪካዊ ምዕራፍ ነው።
ዛሬ በምድራችን ላይ የምናኖረው እያንዳንዱ አረንጓዴ ዐሻራ፣ ዓለም አቀፉን የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖ ከመቋቋም ባለፈ ታላቅ ሀገራዊና አሕጉራዊ የኢኮኖሚ ፋይዳ አለው።
ይህ ግዙፍ ብሔራዊ ንቅናቄ አሁን እንደ ጀመርነው ሀገራዊ ምክክር ሁሉ ልዩነቶቻችንን ወደ ጎን ትተን ኢትዮጵያን በጽኑ መሠረት ላይ ለመገንባት የሚያስችለን ታላቅ ፕሮጀክት ነው።
ቀደም ባሉት ዘመናት እጅግ ሰፊ የደን ሽፋን የነበራት ሀገራችን፣ በሕዝብ ቁጥር መጨመርና በደን ምንጣሮ ምክንያት ሀብቷ ተመናምኖ፣ ለአፈር መሸርሸርና ለግብርና ምርታማነት መቀነስ ተጋልጣ መቆየቷ ይታወሳል።
ይህን ፈተና ለመቀልበስ በ2011 ዓ.ም የተጀመረው የአረንጓዴ ዐሻራ ብሔራዊ ንቅናቄ፣ እስካሁን ከ40 ቢሊዮን በላይ ችግኞችን በመትከል ኢትዮጵያን የአረንጓዴ ልማት ቀዳሚ ተዋናይ አድርጓታል።
በዚህ ንቅናቄ እየተተከሉ ያሉ ችግኞች የደን ዛፎች ብቻ ሳይሆኑ እንደ አቮካዶ፣ ማንጎ፣ ፓፓያ፣ አፕል፣ ቡናና ሻይን የመሳሰሉ ከፍተኛ የኢኮኖሚ ጠቀሜታ ያላቸው በመሆናቸው የአርሶ አደሩን የኑሮ ደረጃ በከፍተኛ ሁኔታ እየቀየሩት ይገኛሉ።
ለሚሊዮኖች የሥራ ዕድል የፈጠረው ይህ ፕሮጀክት ለሀገር በቀል የአግሮ-ፕሮሰሲንግ ኢንዱስትሪዎች ወሳኝ የጥሬ ዕቃ ግብዓት ምንጭ በመሆን ላይ ነው።
የአረንጓዴ ዐሻራ ንቅናቄያችን ከአየር ንብረት ጥበቃና ከምግብ ዋስትና ባሻገር እጅግ ግዙፍ ከሆነው ዓለም አቀፉ የካርበን ገበያ (Carbon Market) በትልቁ ተጠቃሚ እንድንሆን በሩን ከፍቶልናል።
በአረንጓዴ ዐሻራ የምንተክላቸው ቢሊዮን ዛፎች ከከባቢ አየር ውስጥ ከፍተኛ መጠን ያለው በካይ ጋዝ የመምጠጥ አቅም ስላላቸው፣ ለሀገራችን አዲስና ዘላቂ የውጭ ምንዛሬ ማግኛ መስመር እየከፈቱ ነው።
የኢትዮጵያ አረንጓዴ ዐሻራ ቀጣናዊ ትስስርን በማጠናከር ረገድም የጎላ ድርሻ አለው። ለጅቡቲ፣ ለኬንያ፣ ለሶማሊያ እና ለደቡብ ሱዳን በሚሊዮን የሚቆጠሩ ችግኞችን በነፃ በማካፈል የጋራ ዕድገት ራዕያችንን በተግባር እያሳየን እንገኛለን።
ከዚህ ጎን ለጎን መርሐ-ግብሩ እንደ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ያሉ ሜጋ ፕሮጀክቶቻችንን ከጎርፍ እና ከደለል በመጠበቅ የአገልግሎት ዘመናቸውን ያራዝማል።
የሕዝብን ንቁ ተሳትፎ በማረጋገጥ ከ80 በመቶ በላይ የጽድቀት ምጣኔን ያስመዘገበው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ-ግብር ከተለመደው ዓይነት ችግኝ ተከላ በእጅጉ የላቀ አንደምታ ያለው ነው።
አረንጓዴ ዐሻራችን የተፈጥሮ ጸጋችንን በአግባቡ በመጠቀም ለተተኪው ትውልድ የሚበቅል፣ የሚለምልምና የሚጠቅም ሕያው ቅርስ የምናወርስበት የአዲሱ አረንጓዴ ኢኮኖሚያችን ጽኑ መሠረት በመሆኑ፣ ሁላችንም በአንድነት ዐሻራችንን ማኖራችንን እንቀጥል!
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
**********************
(የዕለቱ መልዕከት)
የዘንድሮው ክረምት የሀገራችንን የ50 ቢሊዮን ችግኞች ተከላ ግዙፍ ራዕይ ሙሉ በሙሉ እውን በማድረግ የምናጠናቅቅበት ታሪካዊ ምዕራፍ ነው።
ዛሬ በምድራችን ላይ የምናኖረው እያንዳንዱ አረንጓዴ ዐሻራ፣ ዓለም አቀፉን የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖ ከመቋቋም ባለፈ ታላቅ ሀገራዊና አሕጉራዊ የኢኮኖሚ ፋይዳ አለው።
ይህ ግዙፍ ብሔራዊ ንቅናቄ አሁን እንደ ጀመርነው ሀገራዊ ምክክር ሁሉ ልዩነቶቻችንን ወደ ጎን ትተን ኢትዮጵያን በጽኑ መሠረት ላይ ለመገንባት የሚያስችለን ታላቅ ፕሮጀክት ነው።
ቀደም ባሉት ዘመናት እጅግ ሰፊ የደን ሽፋን የነበራት ሀገራችን፣ በሕዝብ ቁጥር መጨመርና በደን ምንጣሮ ምክንያት ሀብቷ ተመናምኖ፣ ለአፈር መሸርሸርና ለግብርና ምርታማነት መቀነስ ተጋልጣ መቆየቷ ይታወሳል።
ይህን ፈተና ለመቀልበስ በ2011 ዓ.ም የተጀመረው የአረንጓዴ ዐሻራ ብሔራዊ ንቅናቄ፣ እስካሁን ከ40 ቢሊዮን በላይ ችግኞችን በመትከል ኢትዮጵያን የአረንጓዴ ልማት ቀዳሚ ተዋናይ አድርጓታል።
በዚህ ንቅናቄ እየተተከሉ ያሉ ችግኞች የደን ዛፎች ብቻ ሳይሆኑ እንደ አቮካዶ፣ ማንጎ፣ ፓፓያ፣ አፕል፣ ቡናና ሻይን የመሳሰሉ ከፍተኛ የኢኮኖሚ ጠቀሜታ ያላቸው በመሆናቸው የአርሶ አደሩን የኑሮ ደረጃ በከፍተኛ ሁኔታ እየቀየሩት ይገኛሉ።
ለሚሊዮኖች የሥራ ዕድል የፈጠረው ይህ ፕሮጀክት ለሀገር በቀል የአግሮ-ፕሮሰሲንግ ኢንዱስትሪዎች ወሳኝ የጥሬ ዕቃ ግብዓት ምንጭ በመሆን ላይ ነው።
የአረንጓዴ ዐሻራ ንቅናቄያችን ከአየር ንብረት ጥበቃና ከምግብ ዋስትና ባሻገር እጅግ ግዙፍ ከሆነው ዓለም አቀፉ የካርበን ገበያ (Carbon Market) በትልቁ ተጠቃሚ እንድንሆን በሩን ከፍቶልናል።
በአረንጓዴ ዐሻራ የምንተክላቸው ቢሊዮን ዛፎች ከከባቢ አየር ውስጥ ከፍተኛ መጠን ያለው በካይ ጋዝ የመምጠጥ አቅም ስላላቸው፣ ለሀገራችን አዲስና ዘላቂ የውጭ ምንዛሬ ማግኛ መስመር እየከፈቱ ነው።
የኢትዮጵያ አረንጓዴ ዐሻራ ቀጣናዊ ትስስርን በማጠናከር ረገድም የጎላ ድርሻ አለው። ለጅቡቲ፣ ለኬንያ፣ ለሶማሊያ እና ለደቡብ ሱዳን በሚሊዮን የሚቆጠሩ ችግኞችን በነፃ በማካፈል የጋራ ዕድገት ራዕያችንን በተግባር እያሳየን እንገኛለን።
ከዚህ ጎን ለጎን መርሐ-ግብሩ እንደ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ያሉ ሜጋ ፕሮጀክቶቻችንን ከጎርፍ እና ከደለል በመጠበቅ የአገልግሎት ዘመናቸውን ያራዝማል።
የሕዝብን ንቁ ተሳትፎ በማረጋገጥ ከ80 በመቶ በላይ የጽድቀት ምጣኔን ያስመዘገበው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ-ግብር ከተለመደው ዓይነት ችግኝ ተከላ በእጅጉ የላቀ አንደምታ ያለው ነው።
አረንጓዴ ዐሻራችን የተፈጥሮ ጸጋችንን በአግባቡ በመጠቀም ለተተኪው ትውልድ የሚበቅል፣ የሚለምልምና የሚጠቅም ሕያው ቅርስ የምናወርስበት የአዲሱ አረንጓዴ ኢኮኖሚያችን ጽኑ መሠረት በመሆኑ፣ ሁላችንም በአንድነት ዐሻራችንን ማኖራችንን እንቀጥል!
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
23 days ago
የኬንያው የባቡር መስመር ወደ ኢትዮጵያና ደቡብ ሱዳን ሊዘረጋ ነው
#ethiopia | ኬንያ የላፕሴት የልማት ኮሪደር አካል የሆነውን ደረጃውን የጠበቀ የባቡር መስመር ከላሙ ወደ ኢትዮጵያ ለመዘርጋት ማቀዷን ይፋ አደረገች።
ይህ የባቡር መስመር ወደፊትም ወደ ደቡብ ሱዳን የሚቀጥል የትስስር መስመር የሚኖረው ሲሆን በቀጣናው የሚገኙ ከ50 እስከ 60 ሚሊዮን የሚደርሱ ሸማች ገበያቶችን በአንድ ላይ እንደሚያስተሳስር ይጠበቃል።
ይህ ኹነኛ ፕሮጀክት በምስራቅ አፍሪካ አገራት መካከል ያለውን የትራንስፖርት ትስስር ይበልጥ በማጠናከር የቀጠናውን የንግድ ልውውጥ በከፍተኛ ሁኔታ ያሳድገዋል።
ሙሉ በሙሉ ሲጠናቀቅ ወደ 2,900 ኪሎ ሜትር ርዝመት ይኖረዋል ተብሎ የሚጠበቀው ይህ ግዙፍ የባቡር አውታር የሰዎችንና የዕቃዎችን እንቅስቃሴ ቀላልና ፈጣን ከማድረግ ባለፈ ለኢኮኖሚ ዕድገት መፋጠንና ለቀጣናዊ ውህደት ትልቅ መሠረት ይጥላል።
በያፌት ገ/ህይወት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#ethiopia | ኬንያ የላፕሴት የልማት ኮሪደር አካል የሆነውን ደረጃውን የጠበቀ የባቡር መስመር ከላሙ ወደ ኢትዮጵያ ለመዘርጋት ማቀዷን ይፋ አደረገች።
ይህ የባቡር መስመር ወደፊትም ወደ ደቡብ ሱዳን የሚቀጥል የትስስር መስመር የሚኖረው ሲሆን በቀጣናው የሚገኙ ከ50 እስከ 60 ሚሊዮን የሚደርሱ ሸማች ገበያቶችን በአንድ ላይ እንደሚያስተሳስር ይጠበቃል።
ይህ ኹነኛ ፕሮጀክት በምስራቅ አፍሪካ አገራት መካከል ያለውን የትራንስፖርት ትስስር ይበልጥ በማጠናከር የቀጠናውን የንግድ ልውውጥ በከፍተኛ ሁኔታ ያሳድገዋል።
ሙሉ በሙሉ ሲጠናቀቅ ወደ 2,900 ኪሎ ሜትር ርዝመት ይኖረዋል ተብሎ የሚጠበቀው ይህ ግዙፍ የባቡር አውታር የሰዎችንና የዕቃዎችን እንቅስቃሴ ቀላልና ፈጣን ከማድረግ ባለፈ ለኢኮኖሚ ዕድገት መፋጠንና ለቀጣናዊ ውህደት ትልቅ መሠረት ይጥላል።
በያፌት ገ/ህይወት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
26 days ago
የፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ አስተዳደር ኢትዮጵያውያንን ጨምሮ ለስድስት አገራት ዜጎች የተሰጠውን በአሜሪካ የመቆየትና የመሥራት ጊዜያዊ ሕጋዊ ከለላ ለተጨማሪ ቀናት አራዘመ።
የፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ አስተዳደር ኢትዮጵያውያንን ጨምሮ ለስድስት አገራት ዜጎች የተሰጠውን በአሜሪካ የመቆየትና የመሥራት ጊዜያዊ ሕጋዊ ከለላ ለተጨማሪ ቀናት አራዘመ። በአሜሪካ የአገር ውስጥ ደሕንነት መሥሪያ ቤት ሥር የሚገኘው የዜግነትና የፍልሰት አገልግሎት በአገሪቱ ለሚገኙ ኢትዮጵያውያን የተሰጠው ከለላ በመጪው ሐምሌ 10 ቀን 2018 እንደሚያበቃ ትላንት አርብ አስታውቋል።
ከኢትዮጵያ በተጨማሪ ለሶርያ፣ ሶማሊያ፣ የመን፣ ደቡብ ሱዳን እና ምያንማር ዜጎች የተሰጠው ጊዜያዊ ከለላ በተመሣሣይ ቀን ያበቃል። ውሳኔው የሚመለከታቸው የሔቲ ዜጎች ከቀሪዎቹ አምስት አገራት አንድ ሳምንት ቀደም ብሎ በአሜሪካ ለመቆየትና ለመሥራት የሚፈቅድላቸውን ከለላ ያጣሉ።
ይህ ከለላ የተፈጥሮ አደጋ፣ የትጥቅ ግጭት ወይም ሌሎች ያልተለመዱ አስገዳጅ ሁኔታዎች ከገጠማቸው አገራት ወደ አሜሪካ የገቡ ሰዎች በአገሪቱ እንዲቆዩ እና በሕጋዊ መንገድ እንዲሠሩ የሚፈቅ ነው። ከለላው የተሰጣቸው በአሜሪካ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ወደ አገራቸው ቢመለሱ “በግል ደሕንነታቸው ብርቱ ሥጋት አይገጥማቸውም” በሚል አመክንዮ በአገሪቱ የመቆየትና የመሥራት ዕድላቸው እንዲያበቃ የተወሰነው ባለፈው ታኅሳስ 2018 ነበር። ይሁንና ውሳኔው በቦስተን በሚገኝ የማሳቹሴትስ አውራጃ ፍርድ ቤት ታግዷል።
ከኢትዮጵያ በተጨማሪ ሶማሊያና ደቡብ ሱዳንን ጨምሮ የ10 አገራት ዜጎች ተመሳሳይ ሕጋዊ ጥበቃ ነበራቸው። የአሜሪካ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ባለፈው ወር የዶናልድ ትራምፕ አስተዳደር የሔቲና የሶርያ ዜጎች የተሰጠውን ጊዜያዊ ከለላ ማብቃት እንደሚችል ውሳኔ አሳልፏል። የፍርድ ቤቱ ውሳኔ በመቶ ሺሕዎች የሚቆጠሩ ሰዎችን ሕጋዊ ጥበቃ እንደሚያሳጣ የመብት ተሟጋቾችና በአሜሪካ የሚገኙ የተለያዩ ማኅበረሰቦች መሪዎች ሥጋት አላቸው
DW Amharic
የፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ አስተዳደር ኢትዮጵያውያንን ጨምሮ ለስድስት አገራት ዜጎች የተሰጠውን በአሜሪካ የመቆየትና የመሥራት ጊዜያዊ ሕጋዊ ከለላ ለተጨማሪ ቀናት አራዘመ። በአሜሪካ የአገር ውስጥ ደሕንነት መሥሪያ ቤት ሥር የሚገኘው የዜግነትና የፍልሰት አገልግሎት በአገሪቱ ለሚገኙ ኢትዮጵያውያን የተሰጠው ከለላ በመጪው ሐምሌ 10 ቀን 2018 እንደሚያበቃ ትላንት አርብ አስታውቋል።
ከኢትዮጵያ በተጨማሪ ለሶርያ፣ ሶማሊያ፣ የመን፣ ደቡብ ሱዳን እና ምያንማር ዜጎች የተሰጠው ጊዜያዊ ከለላ በተመሣሣይ ቀን ያበቃል። ውሳኔው የሚመለከታቸው የሔቲ ዜጎች ከቀሪዎቹ አምስት አገራት አንድ ሳምንት ቀደም ብሎ በአሜሪካ ለመቆየትና ለመሥራት የሚፈቅድላቸውን ከለላ ያጣሉ።
ይህ ከለላ የተፈጥሮ አደጋ፣ የትጥቅ ግጭት ወይም ሌሎች ያልተለመዱ አስገዳጅ ሁኔታዎች ከገጠማቸው አገራት ወደ አሜሪካ የገቡ ሰዎች በአገሪቱ እንዲቆዩ እና በሕጋዊ መንገድ እንዲሠሩ የሚፈቅ ነው። ከለላው የተሰጣቸው በአሜሪካ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ወደ አገራቸው ቢመለሱ “በግል ደሕንነታቸው ብርቱ ሥጋት አይገጥማቸውም” በሚል አመክንዮ በአገሪቱ የመቆየትና የመሥራት ዕድላቸው እንዲያበቃ የተወሰነው ባለፈው ታኅሳስ 2018 ነበር። ይሁንና ውሳኔው በቦስተን በሚገኝ የማሳቹሴትስ አውራጃ ፍርድ ቤት ታግዷል።
ከኢትዮጵያ በተጨማሪ ሶማሊያና ደቡብ ሱዳንን ጨምሮ የ10 አገራት ዜጎች ተመሳሳይ ሕጋዊ ጥበቃ ነበራቸው። የአሜሪካ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ባለፈው ወር የዶናልድ ትራምፕ አስተዳደር የሔቲና የሶርያ ዜጎች የተሰጠውን ጊዜያዊ ከለላ ማብቃት እንደሚችል ውሳኔ አሳልፏል። የፍርድ ቤቱ ውሳኔ በመቶ ሺሕዎች የሚቆጠሩ ሰዎችን ሕጋዊ ጥበቃ እንደሚያሳጣ የመብት ተሟጋቾችና በአሜሪካ የሚገኙ የተለያዩ ማኅበረሰቦች መሪዎች ሥጋት አላቸው
DW Amharic
Sponsored by
Surafel
26 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የዶናልድ ትራምፕ አስተዳደር በሰብአዊ ጥበቃ መርሃ-ግብር (TPS) ስር አሜሪካ ውስጥ ለሚኖሩ በመቶ ሺዎች ለሚቆጠሩ ስደተኞች የተሰጠው የሥራ ፈቃድ ሊያበቃ ጥቂት ሰዓታት ሲቀሩት ማራዘሚያ መስጠቱን የአሜሪካ ሚዲያዎች ዘግበዋል።
የሥራ ፈቃዱ መቋረጥ ለዓመታት አሜሪካ ውስጥ በሕጋዊ መንገድ ሲኖሩና ሲሰሩ የነበሩ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ የጊዜያዊ መከላከያ ሁኔታ (TPS) ተጠቃሚዎች ሥራቸውንና ገቢያቸውን እንዲያጡ ሊያደርግ ይችል ነበር። ይህ የሥራ ፈቃድ ማራዘሚያ የተሰጠው፣ የአሜሪካ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ባለፈው ወር የትራምፕ አስተዳደር እስከ 1.3 ሚሊዮን ለሚደርሱ ስደተኞች የተሰጠውን ሰብአዊ ጥበቃ እንዲሰርዝ እና በሚቀጥሉት ሳምንታት ውስጥ ወደ ሀገራቸው እንዲባረሩ መንገድ የሚከፍት ውሳኔ ባሳለፈበት ማዕቀፍ ውስጥ ነው።
የአሜሪካ የዜግነት እና የስደተኞች አገልግሎት (USCIS) ባወጣው አዲስ መረጃ መሠረት፣ የሄይቲ ስደተኞች የሥራ ፈቃድ እስከ ጁላይ 24 የተራዘመ ሲሆን፤ የኢትዮጵያ፣ ሚያንማር፣ ደቡብ ሱዳን፣ ሶርያ፣ የመን እና ሶማሊያ የቲፒኤስ (TPS) ተጠቃሚዎች የሥራ ፈቃድ ደግሞ እስከሚቀጥለው ሳምንት ዓርብ ድረስ እንዲያበቃ ተወስኗል።
እነዚህን ሰራተኞች ቀጥረው የሚያሰሩ የተለያዩ ዘርፎች; ከአረጋውያን መንከባከቢያ እና ሆስፒታሎች እስከ ትምህርት ቤቶች እና አውሮፕላን ማረፊያዎች- ከፍተኛ ውጥንቅጥ ውስጥ የገቡ ሲሆን፣ ከትራምፕ አስተዳደር መፍትሄ እንዲሰጣቸው በስተጀርባ እየተማጸኑ ይገኛሉ። እንደ ሰራተኞች ማህበራት መረጃ ከሆነ አንዳንድ ቀጣሪዎች ከዛሬው ዕለት በፊት የቲፒኤስ ባለመብቶችን ከሥራ ማሰናበት ጀምረው ነበር።
የፍሎሪዳ ትልቁ የጤና ጥበቃ ሰራተኞች ማህበር (1199SEIU) መሪ የሆኑት ማርጋሬት ኔሬት በጉዳዩ ላይ ሲናገሩ “በጣም ከፍተኛ የሆነ ግራ መጋባት ነው ያለው፤ እኛ ሰራተኛ ህዝቦች ነን፣ እነሱ ግን እንደ ቆሻሻ እያዩን ነው” ሲሉ ቅሬታቸውን ገልጸዋል።
የሥራ ፈቃዱ መቋረጥ ለዓመታት አሜሪካ ውስጥ በሕጋዊ መንገድ ሲኖሩና ሲሰሩ የነበሩ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ የጊዜያዊ መከላከያ ሁኔታ (TPS) ተጠቃሚዎች ሥራቸውንና ገቢያቸውን እንዲያጡ ሊያደርግ ይችል ነበር። ይህ የሥራ ፈቃድ ማራዘሚያ የተሰጠው፣ የአሜሪካ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ባለፈው ወር የትራምፕ አስተዳደር እስከ 1.3 ሚሊዮን ለሚደርሱ ስደተኞች የተሰጠውን ሰብአዊ ጥበቃ እንዲሰርዝ እና በሚቀጥሉት ሳምንታት ውስጥ ወደ ሀገራቸው እንዲባረሩ መንገድ የሚከፍት ውሳኔ ባሳለፈበት ማዕቀፍ ውስጥ ነው።
የአሜሪካ የዜግነት እና የስደተኞች አገልግሎት (USCIS) ባወጣው አዲስ መረጃ መሠረት፣ የሄይቲ ስደተኞች የሥራ ፈቃድ እስከ ጁላይ 24 የተራዘመ ሲሆን፤ የኢትዮጵያ፣ ሚያንማር፣ ደቡብ ሱዳን፣ ሶርያ፣ የመን እና ሶማሊያ የቲፒኤስ (TPS) ተጠቃሚዎች የሥራ ፈቃድ ደግሞ እስከሚቀጥለው ሳምንት ዓርብ ድረስ እንዲያበቃ ተወስኗል።
እነዚህን ሰራተኞች ቀጥረው የሚያሰሩ የተለያዩ ዘርፎች; ከአረጋውያን መንከባከቢያ እና ሆስፒታሎች እስከ ትምህርት ቤቶች እና አውሮፕላን ማረፊያዎች- ከፍተኛ ውጥንቅጥ ውስጥ የገቡ ሲሆን፣ ከትራምፕ አስተዳደር መፍትሄ እንዲሰጣቸው በስተጀርባ እየተማጸኑ ይገኛሉ። እንደ ሰራተኞች ማህበራት መረጃ ከሆነ አንዳንድ ቀጣሪዎች ከዛሬው ዕለት በፊት የቲፒኤስ ባለመብቶችን ከሥራ ማሰናበት ጀምረው ነበር።
የፍሎሪዳ ትልቁ የጤና ጥበቃ ሰራተኞች ማህበር (1199SEIU) መሪ የሆኑት ማርጋሬት ኔሬት በጉዳዩ ላይ ሲናገሩ “በጣም ከፍተኛ የሆነ ግራ መጋባት ነው ያለው፤ እኛ ሰራተኛ ህዝቦች ነን፣ እነሱ ግን እንደ ቆሻሻ እያዩን ነው” ሲሉ ቅሬታቸውን ገልጸዋል።
1 month ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የሱዳን ጦር ከኢትዮጵያ ድንበር አቅራቢያ በሚገኘውን ኩምሩክ ከተማ ‹‹በጥቂት ሰአታት ውስጥ›› እንደሚቆጣጠር አስታወቀ፡፡ አልሻረቅ አልአውሳት የተሰኘው ጋዜጣ እንደዘገበው በሌተና ጄኔራል አብዱል ፈታህ አልብሩሀን የሚመራው የሱዳን ጦር ሀይል በብሉ ናይል ግዛት ውስጥ በሚገኘው ኩምሩክ ከተማ አካባቢ ከፍተኛ ሀይል እያስገባ ይገኛል፡፡ ወታደራዊ ምንጮቹን ዋቢ ያደረገው ዘገባው እንዳለው ሀይል ማጠናከር ያስፈለገው በተፋላሚው ፈጥኖ ደራሽ ሀይል ታጣቂዎች ምሽግ ላይ እያደረሰ ያለውን የመድፍ ድብደባ ተከትሎ ነው፡፡ በተጨማሪም ድሮኖችን በመጠቀም በተፋላሚው ታጣቂዎች ላይ ጥቃቱን መቀጠሉን ያስታወቀው ዘገባው ይህም የጦር ሀይሉ ወደፊት እንዲገፋ እንዳስቻለው አስታውቋል፡፡
ይህንን ተከትሎም አሁን በከተማው ዙሪያ በሚገኙ መንደሮች ውስጥ የምድር ጦር ፍልሚያ መጀመሩን ጠቅሷል፡፡ ለዚህ ፍልሚያ እንዲረዳው ሀይሉን በማጠናከር ላይ የሚገኘው የሱዳን ጦር ወታደራዊ ምንጮች ጨምረው እንደገለፁት ጦርነቱ በሚቀጥሉት ሰአታት ውስጥ ኩምሩክ ከተማ ውስጥ ዘልቆ እንደሚገባ እምነት አሳድረዋል፡፡ ስለጉዳዩ ከዜና አውታሩ የተጠየቁት የኩምሩክ ከተማ ገዥው አብዱል አቲ አል ፋቂ ሲናገሩ ‹‹ወታደራዊ ድሉ እየተቃረበ ነው›› ካሉ በኋላ ይህ ፍልሚያ በብሉ ናይል ግዛት ውስጥ ፈጥኖ ደራሽ ሀይሉን ጠራርጎ ለማስወጣት ‹‹የመጨረሻው አውደ ግንባር ነው›› ብለዋል፡፡ ጨምረውም የሱዳን ጦርና አጋሮቹ የመንግስትን ክብር ለመመለስና የተነጠቁ አካባቢዎችን ለማስመለስ ቁርጠኛ ሆነው እየተፋለሙ እንደሚገኙ አስረድተዋል፡፡ እንደዘገባው ካለፈው መጋቢት ወር አንስቶ በብሉ ናይል ግዛት ውስጥ የሱዳን ጦር በአንድ በኩል እንዲሁም ፈጥኖ ደራሽ ሀይሉና አጋሮቹ በሌላ በኩል ሆነው ከባድ ጦርነት እያካሄዱ ይገኛሉ፡፡
ይህንን ተከትሎም ፈጥኖ ደራሽ ሀይሉ ከኢትዮጵያና ከደቡብ ሱዳን ጋር የሚዋሰነውን ኩምሩክ ከተማ ለመቆጣጠር ችሎ ነበር፡፡ የከተማው ገዢ የሆኑት አል ፋቂ ለአልሻረቅ አልአውሳት በሰጡት መግለጫ በአካባቢው ያለው የሰብአዊነት ሁኔታ ልዩ ትኩረት የሚያስፈልገው ነው፡፡ በአካባቢው ለወራት በዘለቀው በዚህ ጦርነት ወደ100 ሺህ ያህል ሰዎች መፈናቀላቸውን ጠቅሰው ፈጥኖ ደራሽ ሀይሉ የመብራትና የውሀ መሰረተ ልማቶችንና የጤና አገልግሎት መስጫዎችን በማውደሙ ችግሩን የከፋ እንዳደረገው አስረድተዋል፡፡ እንደዘገባው ኩምሩክ ከተማ በደቡብ ምስራቃዊ ሱዳን በብሉናይል ግዛት ውስጥ የሚገኝና ከኢትዮጵያ ጋር ድንበር የሚዋሰን ነው፡፡
ይህ ከተማ የግዛቱ ዋና ከተማ ከሆነው ዳዝሚን በ200 ኪሎ ሜትር ርቀት ይገኛል፡፡ ከተማው በኢትዮጵያና በሱዳን መካከል የአቅርቦት ሰንሰለት ያለበት በመሆኑ ትልቅ ወታደራዊ ስትራቴጂያዊ ጠቀሜታ እንዳለውም አስረድቷል፡፡
ይህንን ተከትሎም አሁን በከተማው ዙሪያ በሚገኙ መንደሮች ውስጥ የምድር ጦር ፍልሚያ መጀመሩን ጠቅሷል፡፡ ለዚህ ፍልሚያ እንዲረዳው ሀይሉን በማጠናከር ላይ የሚገኘው የሱዳን ጦር ወታደራዊ ምንጮች ጨምረው እንደገለፁት ጦርነቱ በሚቀጥሉት ሰአታት ውስጥ ኩምሩክ ከተማ ውስጥ ዘልቆ እንደሚገባ እምነት አሳድረዋል፡፡ ስለጉዳዩ ከዜና አውታሩ የተጠየቁት የኩምሩክ ከተማ ገዥው አብዱል አቲ አል ፋቂ ሲናገሩ ‹‹ወታደራዊ ድሉ እየተቃረበ ነው›› ካሉ በኋላ ይህ ፍልሚያ በብሉ ናይል ግዛት ውስጥ ፈጥኖ ደራሽ ሀይሉን ጠራርጎ ለማስወጣት ‹‹የመጨረሻው አውደ ግንባር ነው›› ብለዋል፡፡ ጨምረውም የሱዳን ጦርና አጋሮቹ የመንግስትን ክብር ለመመለስና የተነጠቁ አካባቢዎችን ለማስመለስ ቁርጠኛ ሆነው እየተፋለሙ እንደሚገኙ አስረድተዋል፡፡ እንደዘገባው ካለፈው መጋቢት ወር አንስቶ በብሉ ናይል ግዛት ውስጥ የሱዳን ጦር በአንድ በኩል እንዲሁም ፈጥኖ ደራሽ ሀይሉና አጋሮቹ በሌላ በኩል ሆነው ከባድ ጦርነት እያካሄዱ ይገኛሉ፡፡
ይህንን ተከትሎም ፈጥኖ ደራሽ ሀይሉ ከኢትዮጵያና ከደቡብ ሱዳን ጋር የሚዋሰነውን ኩምሩክ ከተማ ለመቆጣጠር ችሎ ነበር፡፡ የከተማው ገዢ የሆኑት አል ፋቂ ለአልሻረቅ አልአውሳት በሰጡት መግለጫ በአካባቢው ያለው የሰብአዊነት ሁኔታ ልዩ ትኩረት የሚያስፈልገው ነው፡፡ በአካባቢው ለወራት በዘለቀው በዚህ ጦርነት ወደ100 ሺህ ያህል ሰዎች መፈናቀላቸውን ጠቅሰው ፈጥኖ ደራሽ ሀይሉ የመብራትና የውሀ መሰረተ ልማቶችንና የጤና አገልግሎት መስጫዎችን በማውደሙ ችግሩን የከፋ እንዳደረገው አስረድተዋል፡፡ እንደዘገባው ኩምሩክ ከተማ በደቡብ ምስራቃዊ ሱዳን በብሉናይል ግዛት ውስጥ የሚገኝና ከኢትዮጵያ ጋር ድንበር የሚዋሰን ነው፡፡
ይህ ከተማ የግዛቱ ዋና ከተማ ከሆነው ዳዝሚን በ200 ኪሎ ሜትር ርቀት ይገኛል፡፡ ከተማው በኢትዮጵያና በሱዳን መካከል የአቅርቦት ሰንሰለት ያለበት በመሆኑ ትልቅ ወታደራዊ ስትራቴጂያዊ ጠቀሜታ እንዳለውም አስረድቷል፡፡
1 month ago
ኢትዮጵያ በቀጣናው ከፍተኛ የገቢ ግብር በመጣል 3ኛ ደረጃ ላይ ተቀመጠች
በአፍሪካ ቀንድ እየተካሄደ ያለውን መጠነ-ሰፊ የፋይናንስ እና የግብር ማሻሻያ ተከትሎ፣ ኢትዮጵያ በምስራቅ አፍሪካ ከሚገኙ ሀገራት መካከል በተቀጣሪ ሰራተኞች ደመወዝ ላይ ከፍተኛ ግብር በመጣል ሶስተኛዋ ሀገር መሆንዋ ታውቋል።
የቀጣናውን የቅጥር ገቢ ግብር (PAYE) ተመን ያነጻጸረው አዲስ ጥናት እንደሚያሳየው፣ የገቢዎች ሚኒስቴር ከፍተኛውን የግብር ተመን 35 በመቶ አድርሶ እየተገበረ ይገኛል። ይህም ግልጽ የሆነ ከፍተኛ የግብር ጫና ካለባትና 40 በመቶ ከምትከፍለው ኡጋንዳ፣ እንዲሁም 35 በመቶ የመጨረሻ የግብር ተመን ካላትና ተጨማሪ ልዩ ልዩ ታክሶችን ከምትጥለው ኬንያ ቀጥሎ ኢትዮጵያን በሶስተኛ ደረጃ ላይ አስቀምጧታል።
ይህ ደረጃ የመጣው ኢትዮጵያ እ.ኤ.አ. በሐምሌ 2025 ያከናወነችውን አጠቃላይ የግብር ማሻሻያ ተከትሎ ነው። መንግስት ቀደም ሲል በሀገር ቁጥጥር ስር የነበረውን የኢኮኖሚ ሞዴል ወደ ነፃ ገበያ ለመቀየር በሚያደርገው ሽግግር፣ የመሠረተ ልማት ጉድለቶችን ለመሙላትና የኢትዮጵያን ብር ለማረጋጋት መደበኛ ተቀጣሪዎችን ዋነኛ የገቢ ምንጭ አድርጓል።
ይህ የደረጃ ምደባ የወጣው ኢትዮጵያ እ.ኤ.አ በሐምሌ 2025 ሰፊ የፊስካል እና የግብር ማሻሻያ ማድረጓን ተከትሎ ነው። መንግስት የኢኮኖሚ ሞዴሉን ከመንግስት ቁጥጥር ወደ ነፃ ገበያ መርህ ለመቀየር በሚያደርገው ጉዞ፣ የመሰረተ ልማት ጉድለቶችን ለመሙላት እና የኢትዮጵያን ብር የመግዛት አቅም ለማረጋጋት በመደበኛው የስራ ዘርፍ ላይ በሚጣል የገቢ ግብር ላይ በእጅጉ ተደግፏል። ይሁን እንጂ የግብር እርከኑ የተቀረጸበት መንገድ መካከለኛ ደረጃ ላይ ያሉ ስራ አስኪያጆች እና ባለሙያዎች በፍጥነት ወደ ከፍተኛው 35 በመቶ የግብር ጣሪያ ውስጥ እንዲገቡ የሚያስገድድ መሆኑን የምጣኔ ሀብት ባለሙያዎች ይናገራሉ።
በአንጻሩ ጎረቤቶቹ ታንዛኒያ እና ሩዋንዳ ከፍተኛውን የገቢ ግብር ተመናቸውን በ30 በመቶ የወሰኑ ሲሆን፣ ደቡብ ሱዳን ደግሞ በ15 በመቶ ዝቅተኛ ታክስ በቀጣናው የመጨረሻውን ደረጃ ይዛለች።
ይህ በምስራቅ አፍሪካ ሀገራት መካከል ያለው የግብር ፖሊሲ ልዩነት በቀጣናው የሰለጠነ የሰው ኃይል ዝውውር ላይ ጫና እየፈጠረ ይገኛል ተብሏል።
Seledadotio
Seledadotio
በአፍሪካ ቀንድ እየተካሄደ ያለውን መጠነ-ሰፊ የፋይናንስ እና የግብር ማሻሻያ ተከትሎ፣ ኢትዮጵያ በምስራቅ አፍሪካ ከሚገኙ ሀገራት መካከል በተቀጣሪ ሰራተኞች ደመወዝ ላይ ከፍተኛ ግብር በመጣል ሶስተኛዋ ሀገር መሆንዋ ታውቋል።
የቀጣናውን የቅጥር ገቢ ግብር (PAYE) ተመን ያነጻጸረው አዲስ ጥናት እንደሚያሳየው፣ የገቢዎች ሚኒስቴር ከፍተኛውን የግብር ተመን 35 በመቶ አድርሶ እየተገበረ ይገኛል። ይህም ግልጽ የሆነ ከፍተኛ የግብር ጫና ካለባትና 40 በመቶ ከምትከፍለው ኡጋንዳ፣ እንዲሁም 35 በመቶ የመጨረሻ የግብር ተመን ካላትና ተጨማሪ ልዩ ልዩ ታክሶችን ከምትጥለው ኬንያ ቀጥሎ ኢትዮጵያን በሶስተኛ ደረጃ ላይ አስቀምጧታል።
ይህ ደረጃ የመጣው ኢትዮጵያ እ.ኤ.አ. በሐምሌ 2025 ያከናወነችውን አጠቃላይ የግብር ማሻሻያ ተከትሎ ነው። መንግስት ቀደም ሲል በሀገር ቁጥጥር ስር የነበረውን የኢኮኖሚ ሞዴል ወደ ነፃ ገበያ ለመቀየር በሚያደርገው ሽግግር፣ የመሠረተ ልማት ጉድለቶችን ለመሙላትና የኢትዮጵያን ብር ለማረጋጋት መደበኛ ተቀጣሪዎችን ዋነኛ የገቢ ምንጭ አድርጓል።
ይህ የደረጃ ምደባ የወጣው ኢትዮጵያ እ.ኤ.አ በሐምሌ 2025 ሰፊ የፊስካል እና የግብር ማሻሻያ ማድረጓን ተከትሎ ነው። መንግስት የኢኮኖሚ ሞዴሉን ከመንግስት ቁጥጥር ወደ ነፃ ገበያ መርህ ለመቀየር በሚያደርገው ጉዞ፣ የመሰረተ ልማት ጉድለቶችን ለመሙላት እና የኢትዮጵያን ብር የመግዛት አቅም ለማረጋጋት በመደበኛው የስራ ዘርፍ ላይ በሚጣል የገቢ ግብር ላይ በእጅጉ ተደግፏል። ይሁን እንጂ የግብር እርከኑ የተቀረጸበት መንገድ መካከለኛ ደረጃ ላይ ያሉ ስራ አስኪያጆች እና ባለሙያዎች በፍጥነት ወደ ከፍተኛው 35 በመቶ የግብር ጣሪያ ውስጥ እንዲገቡ የሚያስገድድ መሆኑን የምጣኔ ሀብት ባለሙያዎች ይናገራሉ።
በአንጻሩ ጎረቤቶቹ ታንዛኒያ እና ሩዋንዳ ከፍተኛውን የገቢ ግብር ተመናቸውን በ30 በመቶ የወሰኑ ሲሆን፣ ደቡብ ሱዳን ደግሞ በ15 በመቶ ዝቅተኛ ታክስ በቀጣናው የመጨረሻውን ደረጃ ይዛለች።
ይህ በምስራቅ አፍሪካ ሀገራት መካከል ያለው የግብር ፖሊሲ ልዩነት በቀጣናው የሰለጠነ የሰው ኃይል ዝውውር ላይ ጫና እየፈጠረ ይገኛል ተብሏል።
Seledadotio
Seledadotio
1 month ago
ከምድር ጥበቃ ወደ ማዕድ በረከት፤ የኢትዮጵያን የደን ሽፋን ያሳደገው የአረንጓዴ ዐሻራ ታሪካዊ ስኬት
************
ዛሬ ዓለማችን በአየር ንብረት ለውጥ ምክንያት የመጣውን የሙቀት መጨመር፣ የሰደድ እሳት፣ የጎርፍ እንዲሁም የድርቅ አደጋዎችን ለመቋቋም በብርቱ ትግል ውስጥ ትገኛለች።
አፍሪካ ለዓለም የሙቀት መጨመር ያበረከተችው አስተዋጽኦ እጅግ አነስተኛ ቢሆንም፣ የችግሩ ቀዳሚ ተጠቂ መሆኗ አልቀረም።
ኢትዮጵያ ይህንን የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖ ለመቀነስ ተግባራዊ እርምጃ በመውሰድ፣ አህጉራዊ እና ዓለም አቀፋዊ ተስፋን ማለምና ለውጥ ማምጣት እንደሚቻል በተግባር እያሳየች ትገኛለች።
በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አነሳሽነት በ2011 ዓ.ም የተጀመረው "የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር" በአሁኑ ወቅት የሀገር ውስጥ ስኬት ብቻ መሆኑ አብቅቶ፣ ለመላው የአፍሪካ አህጉር ብሩህ የተስፋ ስንቅና ታላቅ የተሞክሮ ምንጭ ለመሆን በቅቷል።
መርሐ ግብሩ ከተጀመረበት ጊዜ አንስቶ እስካሁን ድረስ በመላው ኢትዮጵያ ከ48 ቢሊዮን በላይ ችግኞች የተተከሉ ሲሆን፤ ይህም የሀገራችንን የደን ሽፋን በ2010 ዓ.ም ከነበረበት 17.2 በመቶ በአሁኑ ወቅት ወደ 23.6 በመቶ ከፍ እንዲል አድርጎታል።
በዘንድሮው የችግኝ ተከላ ወቅት ደግሞ ኢትዮጵያ ያስቀመጠችውን የ65 ቢሊዮን ታሪካዊ ግብ ለማሳካት በሚያስችል መልኩ ከ8 ቢሊዮን በላይ ችግኞች ዝግጁ ተደርገዋል።
ይህ ዓይነቱ መጠነ-ሰፊ ንቅናቄ የደን ሽፋንን ከማሳደግ ባለፈ፣ የሕዝቡን ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ሕይወት በመለወጥ ረገድ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል።
መርሐ ግብሩ የተራቆቱ መሬቶች እንዲያገግሙ ከማድረጉ ባሻገር፣ እንደ አቮካዶ፣ ማንጎ፣ ፓፓያ እና አፕል ያሉ ለምግብነትና ለገበያ የሚውሉ የፍራፍሬ ችግኞችን በስፋት አካትቷል።
ይህም የዜጎችን የምግብ ዋስትና ለማረጋገጥና የውጭ ምንዛሬ ገቢን ለማሳደግ “ከምድር ጥበቃ ወደ ማዕድ በረከት” የተሻገረ ስትራቴጂ መሆኑን በተግባር አሳይቷል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብርን ሲያስጀምሩ የነበራቸው ራዕይ በሀገር ውስጥ ብቻ የተገደበ አልነበረም።
የአየር ንብረት ለውጥ ድንበር የለሽ በመሆኑ፣ መከላከል የሚቻለውም በጋራና በትብብር ሲሰራ ብቻ እንደሆነ በተደጋጋሚ ገልጸዋል።
በዚህም መሠረት ኢትዮጵያ የቀጣናውን በረሃማነት በጋራ ለመግታት በሚሊዮን የሚቆጠሩ ችግኞችን ለጎረቤት ሀገራት ማለትም ለጂቡቲ፣ ለደቡብ ሱዳንና ለኬንያ አበርክታለች።
ይህ ተግባር የፓን-አፍሪካኒዝም እሴትን በተግባር ያሳየ፣ ለመላው አፍሪካውያን አንድነትና አብሮነት አዲስ ትርጉም የሰጠ አርዓያነት ያለው ስኬት ነው።
የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር አፍሪካውያን የራሳቸውን ችግር በራሳቸው አቅም፣ በጋራና በትብብር መፍታት እንደሚችሉ ያሳዩበት ትልቅ የታሪክ ምዕራፍ ነው።
ኢትዮጵያ ያበሰረችው የአረንጓዴ ተስፋ ብርሃን አህጉሪቱን ከተጋረጠባት የበረሃማነትና የአየር ንብረት መዛባት አደጋ ታድጎ፣ የነገዋን አፍሪካ ውብና ለምለም ለማድረግ የበኩሉን ከፍተኛ ሚና እንደሚጫወት ይጠበቃል።
በላሉ ኢታላ
#greenlegacy #climateaction #greenethiopia #ethiopianbroadcastingcorporation
************
ዛሬ ዓለማችን በአየር ንብረት ለውጥ ምክንያት የመጣውን የሙቀት መጨመር፣ የሰደድ እሳት፣ የጎርፍ እንዲሁም የድርቅ አደጋዎችን ለመቋቋም በብርቱ ትግል ውስጥ ትገኛለች።
አፍሪካ ለዓለም የሙቀት መጨመር ያበረከተችው አስተዋጽኦ እጅግ አነስተኛ ቢሆንም፣ የችግሩ ቀዳሚ ተጠቂ መሆኗ አልቀረም።
ኢትዮጵያ ይህንን የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖ ለመቀነስ ተግባራዊ እርምጃ በመውሰድ፣ አህጉራዊ እና ዓለም አቀፋዊ ተስፋን ማለምና ለውጥ ማምጣት እንደሚቻል በተግባር እያሳየች ትገኛለች።
በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አነሳሽነት በ2011 ዓ.ም የተጀመረው "የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር" በአሁኑ ወቅት የሀገር ውስጥ ስኬት ብቻ መሆኑ አብቅቶ፣ ለመላው የአፍሪካ አህጉር ብሩህ የተስፋ ስንቅና ታላቅ የተሞክሮ ምንጭ ለመሆን በቅቷል።
መርሐ ግብሩ ከተጀመረበት ጊዜ አንስቶ እስካሁን ድረስ በመላው ኢትዮጵያ ከ48 ቢሊዮን በላይ ችግኞች የተተከሉ ሲሆን፤ ይህም የሀገራችንን የደን ሽፋን በ2010 ዓ.ም ከነበረበት 17.2 በመቶ በአሁኑ ወቅት ወደ 23.6 በመቶ ከፍ እንዲል አድርጎታል።
በዘንድሮው የችግኝ ተከላ ወቅት ደግሞ ኢትዮጵያ ያስቀመጠችውን የ65 ቢሊዮን ታሪካዊ ግብ ለማሳካት በሚያስችል መልኩ ከ8 ቢሊዮን በላይ ችግኞች ዝግጁ ተደርገዋል።
ይህ ዓይነቱ መጠነ-ሰፊ ንቅናቄ የደን ሽፋንን ከማሳደግ ባለፈ፣ የሕዝቡን ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ሕይወት በመለወጥ ረገድ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል።
መርሐ ግብሩ የተራቆቱ መሬቶች እንዲያገግሙ ከማድረጉ ባሻገር፣ እንደ አቮካዶ፣ ማንጎ፣ ፓፓያ እና አፕል ያሉ ለምግብነትና ለገበያ የሚውሉ የፍራፍሬ ችግኞችን በስፋት አካትቷል።
ይህም የዜጎችን የምግብ ዋስትና ለማረጋገጥና የውጭ ምንዛሬ ገቢን ለማሳደግ “ከምድር ጥበቃ ወደ ማዕድ በረከት” የተሻገረ ስትራቴጂ መሆኑን በተግባር አሳይቷል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብርን ሲያስጀምሩ የነበራቸው ራዕይ በሀገር ውስጥ ብቻ የተገደበ አልነበረም።
የአየር ንብረት ለውጥ ድንበር የለሽ በመሆኑ፣ መከላከል የሚቻለውም በጋራና በትብብር ሲሰራ ብቻ እንደሆነ በተደጋጋሚ ገልጸዋል።
በዚህም መሠረት ኢትዮጵያ የቀጣናውን በረሃማነት በጋራ ለመግታት በሚሊዮን የሚቆጠሩ ችግኞችን ለጎረቤት ሀገራት ማለትም ለጂቡቲ፣ ለደቡብ ሱዳንና ለኬንያ አበርክታለች።
ይህ ተግባር የፓን-አፍሪካኒዝም እሴትን በተግባር ያሳየ፣ ለመላው አፍሪካውያን አንድነትና አብሮነት አዲስ ትርጉም የሰጠ አርዓያነት ያለው ስኬት ነው።
የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር አፍሪካውያን የራሳቸውን ችግር በራሳቸው አቅም፣ በጋራና በትብብር መፍታት እንደሚችሉ ያሳዩበት ትልቅ የታሪክ ምዕራፍ ነው።
ኢትዮጵያ ያበሰረችው የአረንጓዴ ተስፋ ብርሃን አህጉሪቱን ከተጋረጠባት የበረሃማነትና የአየር ንብረት መዛባት አደጋ ታድጎ፣ የነገዋን አፍሪካ ውብና ለምለም ለማድረግ የበኩሉን ከፍተኛ ሚና እንደሚጫወት ይጠበቃል።
በላሉ ኢታላ
#greenlegacy #climateaction #greenethiopia #ethiopianbroadcastingcorporation
1 month ago
ደብረታቦር ዩኒቨርሲቲ 758 ተማሪዎችን ለ15ኛ ጊዜ አስመረቀ
#ethiopia | የደብረታቦር ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት ዘርፎች ሲያስተምራቸው የቆዩ 758 ተማሪዎችን ለ15ኛ ጊዜ አስመረቀ።
ዩኒቨርሲቲው በመጀመሪያና በሁለተኛ ዲግሪ መርሃ ግብሮች፣ በመደበኛ፣ በኤክስቴንሽን እና በክረምት ፕሮግራሞች ሲያስተምራቸው የቆዩ ተማሪዎችን በተመራቂዎች ቤተሰቦችና በተጋባዥ እንግዶች በተገኙበት ሥነ-ስርዓት አስመርቋል።
በምረቃ ሥነ-ስርዓቱ ላይ የተናገሩት የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ዶ/ር ሰለሞን አበጋዝ፣ ተመራቂዎቹ ከብዙ ጥረትና ትጋት በኋላ ለዚህ ደረጃ መብቃታቸውን አድንቀው፣ ምረቃ የሕይወት አዲስ ምዕራፍ እንጂ መጨረሻ እንዳልሆነ ገልጸዋል። ተመራቂዎችም በሙያቸው ውጤታማ ለመሆን እና ለአገር ልማት አስተዋፅኦ ለማበርከት በትጋት እንዲሰሩ አሳስበዋል።
ፕሬዝዳንቱ ዩኒቨርሲቲው ከትምህርት አገልግሎት በተጨማሪ በምርምርና በማህበረሰብ አገልግሎት ዘርፎች ጉልህ ስራዎችን እያከናወነ መሆኑን ገልጸው፣ የደብረታቦር ከተማ ህዝብ ለተማሪዎችና ለዩኒቨርሲቲው እያደረገ ላለው ድጋፍ ምስጋና አቅርበዋል።
በምረቃው ልዩ ትኩረት የሳቡት ከደቡብ ሱዳን በትምህርት ዕድል መጥተው ትምህርታቸውን ያጠናቀቁ ተማሪዎች ሲሆኑ፣ የተማሪዎቹ ተወካይ በዩኒቨርሲቲውና በአካባቢው ማህበረሰብ ከፍተኛ ድጋፍ እንዳገኙ ገልጻለች። በቆይታቸውም የኢትዮጵያን ባህልና እሴቶች ማወቅ እንደቻሉ ጠቅሳ፣ ይህንን ልምድ ወደ አገራቸው ይዘው እንደሚመለሱ ተናግራለች።
በምረቃ ሥነ-ስርዓቱ ከየኮሌጁና ከየኢንስቲትዩቱ ከፍተኛ ውጤት ላስመዘገቡ ተማሪዎች እውቅናና ሽልማት የተበረከተ ሲሆን፣ ከሴት ተመራቂዎች መካከል የሜዲካል ላቦራቶሪ ሳይንስ ዲፓርትመንት ተማሪ እየሩስ ተቀባ 3.9 ነጥብ በማስመዝገብ ልዩ ተሸላሚ ሆናለች።
በአጠቃላይ የዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ ውጤት ባለቤት የሆነው የሜዲካል ላቦራቶሪ ሳይንስ ተማሪ አሸናፊ ታከለ 3.97 ነጥብ በማስመዝገብ የዋንጫ ተሸላሚ ሆኗል።
ከዩኒቨርሲቲው የተገኘ መረጃ እንደሚያመለክተው፣ ደብረታቦር ዩኒቨርሲቲ እስካሁን ከ32 ሺህ በላይ ተማሪዎችን በተለያዩ የትምህርት መስኮች አስመርቋል።
– ደብረታቦር ኮሙኒኬሽን
#ethiopia | የደብረታቦር ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት ዘርፎች ሲያስተምራቸው የቆዩ 758 ተማሪዎችን ለ15ኛ ጊዜ አስመረቀ።
ዩኒቨርሲቲው በመጀመሪያና በሁለተኛ ዲግሪ መርሃ ግብሮች፣ በመደበኛ፣ በኤክስቴንሽን እና በክረምት ፕሮግራሞች ሲያስተምራቸው የቆዩ ተማሪዎችን በተመራቂዎች ቤተሰቦችና በተጋባዥ እንግዶች በተገኙበት ሥነ-ስርዓት አስመርቋል።
በምረቃ ሥነ-ስርዓቱ ላይ የተናገሩት የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ዶ/ር ሰለሞን አበጋዝ፣ ተመራቂዎቹ ከብዙ ጥረትና ትጋት በኋላ ለዚህ ደረጃ መብቃታቸውን አድንቀው፣ ምረቃ የሕይወት አዲስ ምዕራፍ እንጂ መጨረሻ እንዳልሆነ ገልጸዋል። ተመራቂዎችም በሙያቸው ውጤታማ ለመሆን እና ለአገር ልማት አስተዋፅኦ ለማበርከት በትጋት እንዲሰሩ አሳስበዋል።
ፕሬዝዳንቱ ዩኒቨርሲቲው ከትምህርት አገልግሎት በተጨማሪ በምርምርና በማህበረሰብ አገልግሎት ዘርፎች ጉልህ ስራዎችን እያከናወነ መሆኑን ገልጸው፣ የደብረታቦር ከተማ ህዝብ ለተማሪዎችና ለዩኒቨርሲቲው እያደረገ ላለው ድጋፍ ምስጋና አቅርበዋል።
በምረቃው ልዩ ትኩረት የሳቡት ከደቡብ ሱዳን በትምህርት ዕድል መጥተው ትምህርታቸውን ያጠናቀቁ ተማሪዎች ሲሆኑ፣ የተማሪዎቹ ተወካይ በዩኒቨርሲቲውና በአካባቢው ማህበረሰብ ከፍተኛ ድጋፍ እንዳገኙ ገልጻለች። በቆይታቸውም የኢትዮጵያን ባህልና እሴቶች ማወቅ እንደቻሉ ጠቅሳ፣ ይህንን ልምድ ወደ አገራቸው ይዘው እንደሚመለሱ ተናግራለች።
በምረቃ ሥነ-ስርዓቱ ከየኮሌጁና ከየኢንስቲትዩቱ ከፍተኛ ውጤት ላስመዘገቡ ተማሪዎች እውቅናና ሽልማት የተበረከተ ሲሆን፣ ከሴት ተመራቂዎች መካከል የሜዲካል ላቦራቶሪ ሳይንስ ዲፓርትመንት ተማሪ እየሩስ ተቀባ 3.9 ነጥብ በማስመዝገብ ልዩ ተሸላሚ ሆናለች።
በአጠቃላይ የዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ ውጤት ባለቤት የሆነው የሜዲካል ላቦራቶሪ ሳይንስ ተማሪ አሸናፊ ታከለ 3.97 ነጥብ በማስመዝገብ የዋንጫ ተሸላሚ ሆኗል።
ከዩኒቨርሲቲው የተገኘ መረጃ እንደሚያመለክተው፣ ደብረታቦር ዩኒቨርሲቲ እስካሁን ከ32 ሺህ በላይ ተማሪዎችን በተለያዩ የትምህርት መስኮች አስመርቋል።
– ደብረታቦር ኮሙኒኬሽን
1 month ago
ከሕዳሴው ግድብ ቀጥሎ መላው ኢትዮጵያዊ በአንድ ፅኑ ሐሳብ የተመመበት የአረንጓዴ አሻራ ንቅናቄ
*******************
በ2011 ዓ.ም የተጀመረውና ላለፉት ሰባት ዓመታት በተከታታይ ከሕፃናት እስከ አዋቂ ከ20 ሚሊዮን በላይ ዜጎችን በብሔራዊ ንቅናቄ ያሳተፈው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር፣ በሀገሪቱ ሁለንተናዊ ገጽታ ላይ ታሪካዊና ተጨባጭ ለውጦችን እያስመዘገበ ይገኛል። እስካሁን ባለው ሂደት በመላው ሀገሪቱ ወደ 48 ቢሊዮን የሚጠጉ ችግኞች የተተከሉ ሲሆን፣ ይህም የሀገሪቱን የደን ሽፋን ከነበረበት 17.2 በመቶ ወደ 23.6 በመቶ ከፍ እንዲል አድርጎታል።
ይህ መርሃ-ግብር በሥነ-ምህዳርና በውሃ ሀብት ጥበቃ ላይ ያመጣው ተፅዕኖ ከፍተኛ ሲሆን፣ በተለይም ላለፉት 18 ዓመታት ደርቆ የነበረው የሐሮማያ ሐይቅ እና ከስምጥ ሸለቆ ሐይቆች አንዱ የሆነው የአባያ ሐይቅ እንዲያገግሙ አስችሏል። ከዚህም በተጨማሪ የተቆፈሩት ዘጠኝ አኃዝ ያላቸው ጉድጓዶች እንደ ሰው ሠራሽ የውሃ ማጠራቀሚያ ጋን በመሆን ውሃ ወደ መሬት እንዲሰርግ በማድረጋቸው፣ የከርሰ-ምድር ውሃ መጠን እንዲጨምርና ደርቀው የነበሩ ምንጮች ዳግም እንዲፈልቁ ምክንያት ሆኗል።
በአረንጓዴ አሻራው የምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥ አኳያም መርሃ-ግብሩ እንደ አቮካዶ ባሉ ለምግብነት፣ ለንብ ማነብ፣ ለኢኮኖሚ ጠቀሜታና ለውጭ ገበያ የሚውሉ የፍራፍሬ ዝርያዎች በብዛት አንዲመረቱ በማስቻልም ረገድ ትልቅ እገዛ አድርጓል።
በቀጣናዊና ዓለም አቀፋዊ መድረኮችም ኢትዮጵያ የአብዛኞቹ የጎረቤት ሀገራት የውሃ መነሻ በመሆኗ፣ የምታከናውነው የተፋሰስ ልማት የቀጠናውን የውሃ ፍላጎት ለማዳረስ ከፍተኛ ሚና እያበረከተ ይገኛል። በዚህም ለአረንጓዴ ዲፕሎማሲ ማሳያ የሚሆን የችግኝና የልምድ አካፍሎት ለጅቡቲ፣ ለደቡብ ሱዳንና ለኬንያ የተደረገ ሲሆን፣ ከዛምቤዚ ሪቨር ኮርስ ኮሚሽን የተውጣጡ የ7 ሀገራት ልዑካንም የኢትዮጵያን ተሞክሮ ወስደዋል።
በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት፣ በዓለም ኢኮኖሚ ፎረም እና በምግብና እርሻ ድርጅት (FAO) 80ኛ ዓመት የምሥረታ በዓል ላይ የኢትዮጵያ አረንጓዴ አሻራ ከፍተኛ ዓለም አቀፍ እውቅናን አትርፏል።
ከፖለቲካና ከግል ጥቅም ባለፈ ከ“እኔ” ይልቅ ለ“እኛ” የሚያስብ ብሔራዊ እሴት ሆኖ የዳበረው ይህ መርሃ-ግብር፣ በገጠርም በከተማም ሠራተኞች ከአለቆቻቸው ጋር በአንድነት ወጥተው የሚተክሉበትና የሚወያዩበት መድረክ በመፍጠሩ ተቋማዊ ተግባቦትን አጎልብቷል። በዚህም ከሕዳሴ ግድብ ቀጥሎ መላው ኢትዮጵያዊ በአንድ ፅኑ ሀሳብ የተመመበት ትልቁ የጋራ መግባባት መርሃ-ግብር ተደርጎ ይወሰዳል።
በብሌን ደምበሎ
#ethiopianbroadcastingcorporation #ethiopia #greenlegacy #climateaction #ecorestoration
*******************
በ2011 ዓ.ም የተጀመረውና ላለፉት ሰባት ዓመታት በተከታታይ ከሕፃናት እስከ አዋቂ ከ20 ሚሊዮን በላይ ዜጎችን በብሔራዊ ንቅናቄ ያሳተፈው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር፣ በሀገሪቱ ሁለንተናዊ ገጽታ ላይ ታሪካዊና ተጨባጭ ለውጦችን እያስመዘገበ ይገኛል። እስካሁን ባለው ሂደት በመላው ሀገሪቱ ወደ 48 ቢሊዮን የሚጠጉ ችግኞች የተተከሉ ሲሆን፣ ይህም የሀገሪቱን የደን ሽፋን ከነበረበት 17.2 በመቶ ወደ 23.6 በመቶ ከፍ እንዲል አድርጎታል።
ይህ መርሃ-ግብር በሥነ-ምህዳርና በውሃ ሀብት ጥበቃ ላይ ያመጣው ተፅዕኖ ከፍተኛ ሲሆን፣ በተለይም ላለፉት 18 ዓመታት ደርቆ የነበረው የሐሮማያ ሐይቅ እና ከስምጥ ሸለቆ ሐይቆች አንዱ የሆነው የአባያ ሐይቅ እንዲያገግሙ አስችሏል። ከዚህም በተጨማሪ የተቆፈሩት ዘጠኝ አኃዝ ያላቸው ጉድጓዶች እንደ ሰው ሠራሽ የውሃ ማጠራቀሚያ ጋን በመሆን ውሃ ወደ መሬት እንዲሰርግ በማድረጋቸው፣ የከርሰ-ምድር ውሃ መጠን እንዲጨምርና ደርቀው የነበሩ ምንጮች ዳግም እንዲፈልቁ ምክንያት ሆኗል።
በአረንጓዴ አሻራው የምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥ አኳያም መርሃ-ግብሩ እንደ አቮካዶ ባሉ ለምግብነት፣ ለንብ ማነብ፣ ለኢኮኖሚ ጠቀሜታና ለውጭ ገበያ የሚውሉ የፍራፍሬ ዝርያዎች በብዛት አንዲመረቱ በማስቻልም ረገድ ትልቅ እገዛ አድርጓል።
በቀጣናዊና ዓለም አቀፋዊ መድረኮችም ኢትዮጵያ የአብዛኞቹ የጎረቤት ሀገራት የውሃ መነሻ በመሆኗ፣ የምታከናውነው የተፋሰስ ልማት የቀጠናውን የውሃ ፍላጎት ለማዳረስ ከፍተኛ ሚና እያበረከተ ይገኛል። በዚህም ለአረንጓዴ ዲፕሎማሲ ማሳያ የሚሆን የችግኝና የልምድ አካፍሎት ለጅቡቲ፣ ለደቡብ ሱዳንና ለኬንያ የተደረገ ሲሆን፣ ከዛምቤዚ ሪቨር ኮርስ ኮሚሽን የተውጣጡ የ7 ሀገራት ልዑካንም የኢትዮጵያን ተሞክሮ ወስደዋል።
በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት፣ በዓለም ኢኮኖሚ ፎረም እና በምግብና እርሻ ድርጅት (FAO) 80ኛ ዓመት የምሥረታ በዓል ላይ የኢትዮጵያ አረንጓዴ አሻራ ከፍተኛ ዓለም አቀፍ እውቅናን አትርፏል።
ከፖለቲካና ከግል ጥቅም ባለፈ ከ“እኔ” ይልቅ ለ“እኛ” የሚያስብ ብሔራዊ እሴት ሆኖ የዳበረው ይህ መርሃ-ግብር፣ በገጠርም በከተማም ሠራተኞች ከአለቆቻቸው ጋር በአንድነት ወጥተው የሚተክሉበትና የሚወያዩበት መድረክ በመፍጠሩ ተቋማዊ ተግባቦትን አጎልብቷል። በዚህም ከሕዳሴ ግድብ ቀጥሎ መላው ኢትዮጵያዊ በአንድ ፅኑ ሀሳብ የተመመበት ትልቁ የጋራ መግባባት መርሃ-ግብር ተደርጎ ይወሰዳል።
በብሌን ደምበሎ
#ethiopianbroadcastingcorporation #ethiopia #greenlegacy #climateaction #ecorestoration
Sponsored by
Surafel
1 month ago
ኢትዮጵያ ታከናውናለች፡- ስኬታማ ዲፕሎማሲ
************************
"ኢትዮጵያ ወደፊት ለመመንጠቅ (to leap) ቆርጣ የተነሳች ሀገር ናት" ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በንግግራቸው መክፈቻ ላይ ያነሱት ሀሳብ፣ ሀገራችን በዲፕሎማሲው መስክ እያስመዘገበች ያለውን ስኬት ቁልጭ አድርጎ ያሳያል።
እጅግ ተለዋዋጭና በኃያላን ፉክክር በተሞላው የዓለም አቀፍ ፖለቲካ ውስጥ፣ ኢትዮጵያ "የመደመር" እሳቤን በመከተል ፈተናዎችን ወደ ድል እየቀየረች፣ የዓለምን መድረክ በብቃት እየመራች ትገኛለች።
የኢትዮጵያን ዲፕሎማሲ የቀየረው መሠረታዊ የሪፎርም አቅጣጫ፣ የውጭ ግንኙነትን በጥርጣሬና በስጋት ላይ ከተመሠረተ "የህልውና መር" (Survival-driven) አካሄድ አውጥቶ፣ ትብብርንና የጋራ ተጠቃሚነትን ወደሚያስቀድም "የልዕልና መር" (Excellence-driven) አቅጣጫ ማሸጋገሩ ነው።
ብልፅግና ፓርቲ፣ የውጭ ግንኙነት በአንድ ኃያል ወገን ደጋፊ መሆን ላይ ሳይመሰረት፣ "ለራሳችን ኃያል መሆንን" ማዕከል ያደረገ ነፃና ሚዛናዊ የዲፕሎማሲ አቅጣጫ ይከተላል።
ይህ መደመራዊ የውጭ ግንኙነት ፍልስፍና፣ አገራት በውጭ ግንኙነታቸው ከፉክክር ይልቅ ትብብርን እንዲመርጡ፣ የቅርብም ሆነ የሩቅ አገሮችን በባላንጣነት ከመፈረጅ ወጥተው ፍላጎቶቻቸውን በሰከነ ንግግር እንዲያስጠብቁ የሚያደርግ ጥበብ ነው።
በዚህ የሪፎርም አቅጣጫ ከተመዘገቡት ታላላቅ የዲፕሎማሲ ድሎች መካከል፣ የኢትዮጵያ የBRICS (ብሪክስ) ሙሉ አባል መሆን በግንባር ቀደምትነት ይጠቀሳል። ከ40 በላይ አገራት ለአባልነት በጠየቁበት መድረክ ተመራጭ መሆን መቻላችን፣ ጠቅላይ ሚኒስትሩ እንዳሉት ኢትዮጵያ "ዝቅተኛ ግምቶችን ሰብራ" እንደምትነሳ ያሳየ ታሪካዊ እምርታ ነው።
ይህ አባልነት ለሀገራችን ሰፊ የኢንቨስትመንትና የገበያ ዕድል የፈጠረ የዲፕሎማሲ ብስለት ማሳያ ነው።
ሁለተኛው ታላቅ ድል፣ የሕዳሴ ግድብን በስኬት ማጠናቀቅ እና የአባይ ወንዝ የትብብር ማዕቀፍ ስምምነትን (CFA) ወደ ሥራ ማስገባት ነው።
ጉዳዩን ወደ ተ.መ.ድ. የጸጥታው ምክር ቤት በመውሰድ አገራችንን ምክንያታዊ ላልሆነ ጫና ሲዳርግ የነበረውን እንቅስቃሴ፣ "ለአፍሪካዊ ችግር አፍሪካዊ መፍትሔ" በሚል መርህ በዲፕሎማሲያዊ ጥበብ መመከት ተችሏል።
ይህ ስኬት ኢትዮጵያ የመበልጸግ ፍላጎቷ ፊት የሚቆም ማናቸውንም ኃይል እንደማትታገስ ግልጽ መልዕክት ያስተላለፈ፣ "የአፍሪካ ራሷን የመቻል ምልክት" ሆኖ የተመዘገበ ነው።
በተጨማሪም የባሕር በር ባለቤትነትና ተጠቃሚነት አጀንዳን ከተዳፈነበት በማውጣት፣ ኢትዮጵያ ከነበረችበት የጂኦ-ስትራተጂካዊ ጥገኝነት እንድትወጣና የዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ለፍትሐዊ ጥያቄዋ እውቅና እንዲሰጥ ማድረግ ተችሏል።
በ"ዜጋ ተኮር ዲፕሎማሲ" ደግሞ፣ በመካከለኛው ምስራቅና አውሮፓ ካሉ በርካታ ሀገራት ጋር የሥራ ስምሪት ስምምነቶችን በመፈረም፣ ለዜጎቻችን ሰፊ የሥራ ዕድል መፍጠርና በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የነበሩ ከ500 ሺህ በላይ ዜጎችን ወደ ሀገራቸው በክብር መመለስ ተችሏል።
በአረንጓዴ አሻራ ባስመዘገብነው ውጤት COP32ን ለማዘጋጀት መመረጣችን፣ እንዲሁም ለሱዳን እና ደቡብ ሱዳን ሰላም የሰራነው አኩሪ የሽምግልና ሥራ፣ ኢትዮጵያ የአፍሪካ የሰላምና የዲፕሎማሲ ማዕከልነቷን እንዳጸናች ያሳያል።
በእርግጥም ጠቅላይ ሚኒስትሩ እንዳሉት "ከለውጡ በስተጀርባ የዜጎች ሕይወት እየተቀየረ ነው"፤ ይህ የኢትዮጵያ ስኬታማ ዲፕሎማሲም ሀገራችንን ወደ አዲስ የብልጽግና ከፍታ የሚያሸጋግራት ኃያል ክንድ ሆኗል!
በአዶኒያስ ወልደአረጋይ
Ethiopian Broadcasting Corporation #ኢትዮጵያ #ዲፕሎማሲ
************************
"ኢትዮጵያ ወደፊት ለመመንጠቅ (to leap) ቆርጣ የተነሳች ሀገር ናት" ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በንግግራቸው መክፈቻ ላይ ያነሱት ሀሳብ፣ ሀገራችን በዲፕሎማሲው መስክ እያስመዘገበች ያለውን ስኬት ቁልጭ አድርጎ ያሳያል።
እጅግ ተለዋዋጭና በኃያላን ፉክክር በተሞላው የዓለም አቀፍ ፖለቲካ ውስጥ፣ ኢትዮጵያ "የመደመር" እሳቤን በመከተል ፈተናዎችን ወደ ድል እየቀየረች፣ የዓለምን መድረክ በብቃት እየመራች ትገኛለች።
የኢትዮጵያን ዲፕሎማሲ የቀየረው መሠረታዊ የሪፎርም አቅጣጫ፣ የውጭ ግንኙነትን በጥርጣሬና በስጋት ላይ ከተመሠረተ "የህልውና መር" (Survival-driven) አካሄድ አውጥቶ፣ ትብብርንና የጋራ ተጠቃሚነትን ወደሚያስቀድም "የልዕልና መር" (Excellence-driven) አቅጣጫ ማሸጋገሩ ነው።
ብልፅግና ፓርቲ፣ የውጭ ግንኙነት በአንድ ኃያል ወገን ደጋፊ መሆን ላይ ሳይመሰረት፣ "ለራሳችን ኃያል መሆንን" ማዕከል ያደረገ ነፃና ሚዛናዊ የዲፕሎማሲ አቅጣጫ ይከተላል።
ይህ መደመራዊ የውጭ ግንኙነት ፍልስፍና፣ አገራት በውጭ ግንኙነታቸው ከፉክክር ይልቅ ትብብርን እንዲመርጡ፣ የቅርብም ሆነ የሩቅ አገሮችን በባላንጣነት ከመፈረጅ ወጥተው ፍላጎቶቻቸውን በሰከነ ንግግር እንዲያስጠብቁ የሚያደርግ ጥበብ ነው።
በዚህ የሪፎርም አቅጣጫ ከተመዘገቡት ታላላቅ የዲፕሎማሲ ድሎች መካከል፣ የኢትዮጵያ የBRICS (ብሪክስ) ሙሉ አባል መሆን በግንባር ቀደምትነት ይጠቀሳል። ከ40 በላይ አገራት ለአባልነት በጠየቁበት መድረክ ተመራጭ መሆን መቻላችን፣ ጠቅላይ ሚኒስትሩ እንዳሉት ኢትዮጵያ "ዝቅተኛ ግምቶችን ሰብራ" እንደምትነሳ ያሳየ ታሪካዊ እምርታ ነው።
ይህ አባልነት ለሀገራችን ሰፊ የኢንቨስትመንትና የገበያ ዕድል የፈጠረ የዲፕሎማሲ ብስለት ማሳያ ነው።
ሁለተኛው ታላቅ ድል፣ የሕዳሴ ግድብን በስኬት ማጠናቀቅ እና የአባይ ወንዝ የትብብር ማዕቀፍ ስምምነትን (CFA) ወደ ሥራ ማስገባት ነው።
ጉዳዩን ወደ ተ.መ.ድ. የጸጥታው ምክር ቤት በመውሰድ አገራችንን ምክንያታዊ ላልሆነ ጫና ሲዳርግ የነበረውን እንቅስቃሴ፣ "ለአፍሪካዊ ችግር አፍሪካዊ መፍትሔ" በሚል መርህ በዲፕሎማሲያዊ ጥበብ መመከት ተችሏል።
ይህ ስኬት ኢትዮጵያ የመበልጸግ ፍላጎቷ ፊት የሚቆም ማናቸውንም ኃይል እንደማትታገስ ግልጽ መልዕክት ያስተላለፈ፣ "የአፍሪካ ራሷን የመቻል ምልክት" ሆኖ የተመዘገበ ነው።
በተጨማሪም የባሕር በር ባለቤትነትና ተጠቃሚነት አጀንዳን ከተዳፈነበት በማውጣት፣ ኢትዮጵያ ከነበረችበት የጂኦ-ስትራተጂካዊ ጥገኝነት እንድትወጣና የዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ለፍትሐዊ ጥያቄዋ እውቅና እንዲሰጥ ማድረግ ተችሏል።
በ"ዜጋ ተኮር ዲፕሎማሲ" ደግሞ፣ በመካከለኛው ምስራቅና አውሮፓ ካሉ በርካታ ሀገራት ጋር የሥራ ስምሪት ስምምነቶችን በመፈረም፣ ለዜጎቻችን ሰፊ የሥራ ዕድል መፍጠርና በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የነበሩ ከ500 ሺህ በላይ ዜጎችን ወደ ሀገራቸው በክብር መመለስ ተችሏል።
በአረንጓዴ አሻራ ባስመዘገብነው ውጤት COP32ን ለማዘጋጀት መመረጣችን፣ እንዲሁም ለሱዳን እና ደቡብ ሱዳን ሰላም የሰራነው አኩሪ የሽምግልና ሥራ፣ ኢትዮጵያ የአፍሪካ የሰላምና የዲፕሎማሲ ማዕከልነቷን እንዳጸናች ያሳያል።
በእርግጥም ጠቅላይ ሚኒስትሩ እንዳሉት "ከለውጡ በስተጀርባ የዜጎች ሕይወት እየተቀየረ ነው"፤ ይህ የኢትዮጵያ ስኬታማ ዲፕሎማሲም ሀገራችንን ወደ አዲስ የብልጽግና ከፍታ የሚያሸጋግራት ኃያል ክንድ ሆኗል!
በአዶኒያስ ወልደአረጋይ
Ethiopian Broadcasting Corporation #ኢትዮጵያ #ዲፕሎማሲ
1 month ago
ኢትዮጵያ ለዓለም ያበረከተችው ተሞክሮ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 16፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር በዓለም አቀፍ ደረጃ እውቅና እና ተቀባይነት ከማግኘት ባለፈ በተለያዩ ሀገራት ዘንድ እንደተሞክሮ እየተወሰደ ይገኛል፡፡
ለአካባቢ ጥበቃና ለአየር ንብረት ለውጥ መፍትሔ ለመስጠት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በ2011 ዓ.ም የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብርን ካስጀመሩበት ጊዜ አንስቶ እስካሁን 48 ቢሊየን ችግኞች መተከላቸውን የግብርና ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል፡፡
ለተከታታይ ሰባት ዓመታት የተካሄደው መርሐ ግብሩ በኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን እና የኢኮኖሚ እድገትን ከማረጋገጥ ባለፈ የደን ሽፋንን በመጨመር ለአየር ንብረት ለውጥ ተጨባጭ መፍትሔ ሰጥቷል፡፡
የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር የተራቆቱ አካባቢዎችን መልሶ በማቋቋም የኢኮኖሚ ትስስሩን የበለጠ ያጠናከረ ሲሆን÷ ለበርካታ ኢትዮጵያውያን ወጣቶችም የሥራ እድል ፈጥሯል፡፡
ኢትዮጵያ የጀመረችው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር እንደ የዓለም ምግብ እና እርሻ ድርጅት (ፋኦ) በመሳሰሉ ተቋማት እውቅና ያገኘ ሲሆን÷ በሀገራት ዘንድ ደግሞ እንደ መልካም ተሞክሮ እየተወሰደ ይገኛል፡፡
ኢትዮጵያ መርሐ ግብሩን ባስጀመረች ማግስት ለጅቡቲ፣ ደቡብ ሱዳን፣ ኬንያ እና ሱዳን ችግኞችን በመላክ የአካባቢ ጥበቃ ጥረቷን ድንበር ተሻጋሪ ማድረግ ችላለች፡፡
በተመሳሳይ ፓኪስታን ባለፈው ዓመት ኢትዮጵያን የአረንጓዴ ዐሻራ ስትራቴጂያዊ አጋር በማድረግ በአካባቢ ጥበቃ ዘርፍ ከኢትዮጵያ ልምድ ለመውሰድ ስምምነት አድርጋለች፡፡
ይህንን ተከትሎም ኢትዮጵያ በሀገር ውስጥ ውጤት ያመጣውን የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር በማስፋፋት ለአረንጓዴ ዲፕሎማሲ የሰጠችው ትኩረት ውጤት እያመጣ ይገኛል።
ይህ ውጤት ኢትዮጵያ በአፍሪካ እና በዓለም አቀፍ መድረክ የአረንጓዴ ዲፕሎማሲ ግንባር ቀደም ተዋናይ እንድትሆን አስችሏታል።
ዘንድሮም የተያዘውን የ8 ቢሊየን ችግኞች የመትከል ግብ ለማሳካት በሚደረገው ብሔራዊ የንቅናቄ ላይ ኢትዮጵያውያን ለተግባራዊነቱ እንዲረባረቡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጥሪ ማቅረባቸው ይታወሳል፡፡
በሚኪያስ አየለ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 16፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር በዓለም አቀፍ ደረጃ እውቅና እና ተቀባይነት ከማግኘት ባለፈ በተለያዩ ሀገራት ዘንድ እንደተሞክሮ እየተወሰደ ይገኛል፡፡
ለአካባቢ ጥበቃና ለአየር ንብረት ለውጥ መፍትሔ ለመስጠት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በ2011 ዓ.ም የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብርን ካስጀመሩበት ጊዜ አንስቶ እስካሁን 48 ቢሊየን ችግኞች መተከላቸውን የግብርና ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል፡፡
ለተከታታይ ሰባት ዓመታት የተካሄደው መርሐ ግብሩ በኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን እና የኢኮኖሚ እድገትን ከማረጋገጥ ባለፈ የደን ሽፋንን በመጨመር ለአየር ንብረት ለውጥ ተጨባጭ መፍትሔ ሰጥቷል፡፡
የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር የተራቆቱ አካባቢዎችን መልሶ በማቋቋም የኢኮኖሚ ትስስሩን የበለጠ ያጠናከረ ሲሆን÷ ለበርካታ ኢትዮጵያውያን ወጣቶችም የሥራ እድል ፈጥሯል፡፡
ኢትዮጵያ የጀመረችው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር እንደ የዓለም ምግብ እና እርሻ ድርጅት (ፋኦ) በመሳሰሉ ተቋማት እውቅና ያገኘ ሲሆን÷ በሀገራት ዘንድ ደግሞ እንደ መልካም ተሞክሮ እየተወሰደ ይገኛል፡፡
ኢትዮጵያ መርሐ ግብሩን ባስጀመረች ማግስት ለጅቡቲ፣ ደቡብ ሱዳን፣ ኬንያ እና ሱዳን ችግኞችን በመላክ የአካባቢ ጥበቃ ጥረቷን ድንበር ተሻጋሪ ማድረግ ችላለች፡፡
በተመሳሳይ ፓኪስታን ባለፈው ዓመት ኢትዮጵያን የአረንጓዴ ዐሻራ ስትራቴጂያዊ አጋር በማድረግ በአካባቢ ጥበቃ ዘርፍ ከኢትዮጵያ ልምድ ለመውሰድ ስምምነት አድርጋለች፡፡
ይህንን ተከትሎም ኢትዮጵያ በሀገር ውስጥ ውጤት ያመጣውን የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር በማስፋፋት ለአረንጓዴ ዲፕሎማሲ የሰጠችው ትኩረት ውጤት እያመጣ ይገኛል።
ይህ ውጤት ኢትዮጵያ በአፍሪካ እና በዓለም አቀፍ መድረክ የአረንጓዴ ዲፕሎማሲ ግንባር ቀደም ተዋናይ እንድትሆን አስችሏታል።
ዘንድሮም የተያዘውን የ8 ቢሊየን ችግኞች የመትከል ግብ ለማሳካት በሚደረገው ብሔራዊ የንቅናቄ ላይ ኢትዮጵያውያን ለተግባራዊነቱ እንዲረባረቡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጥሪ ማቅረባቸው ይታወሳል፡፡
በሚኪያስ አየለ
2 months ago
ኢትዮጵያን በዓለም አቀፍ የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ተምሳሌት ያደረገው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 9፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የአረንጓዴ ዐሻራ ሀገራዊ ንቅናቄ የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት ከማረጋገጥ እና ብልጽግናን ከማምጣት የረጅም ጊዜ ሀገራዊ ሕልም ጋር በቀጥታ የተቆራኘ አንኳር ጉዳይ ነው።
የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር ኢትዮጵያን በዓለም አቀፍ ደረጃ አርዓያ ያደረገ እና የምትታወቅበት መገለጫ ሆኗል፡፡
መርሐ ግብሩ የተመጣጠነ ዝናብ እንዲኖር፣ ከተፈጥሮ ጋር ተስማምቶ ለመኖር እና በምግብ ራስን ለመቻል ትልቅ እገዛ እያደረገም ይገኛል፡፡
ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የአረንጓዴ ዐሻራ ተግባራት እንደ ሀገር በተጨባጭ የደን መመናመንን በማስቀረት ሽፋኑን ማሳደግ ተችሏል፡፡
ለካርበን ሽያጭና ዛፍ መትከል ስለሚያስገኘው የቢሊየን ዶላሮች የኢኮኖሚ ምንጭ ማወቅ የአሁኑ ዘመን የሕልውና እና የብልጽግና መሠረትን ለመረዳት ወሳኝ መነሻ ነው።
አረንጓዴ ዐሻራ የዓለም አቀፉን የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖ ከመቋቋም ባለፈ ታላቅ ሀገራዊና አሕጉራዊ ፋይዳ ያለው ሲሆን÷ ይህ ታሪካዊ መርሐ ግብር ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ መድረክ ያላትን ተጽዕኖ ፈጣሪነት በማሳደግ አዲስ የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ምዕራፍ ከፍቷል፡፡
በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አነሳሽነት የተጀመረው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር ጊዜያዊ ዘመቻ ሳይሆን የሀገርን የነገ ዕጣ ፈንታ የሚወስን ሆኖ ቀጥሏል።
በዚህም ከፍተኛ የኢኮኖሚ ጠቀሜታ ያላቸውና የምግብ ዋስትናን በተግባር የሚያረጋግጡ የፍራፍሬ ዝርያዎችን ጨምሮ የተለያዩ ችግኞች በመተከላቸው የአርሶ አደሩን የኑሮ ደረጃ በከፍተኛ ሁኔታ እየቀየሩ ይገኛሉ።
ከተከላው ጎን ለጎን ችግኞችን በማፍላትና በመንከባከብ ሂደት ውስጥ ለሚሊየኖች ሰፊ የሥራ ዕድል ተፈጥሯል።
በአረንጓዴ ዐሻራ የሚተከሉ ችግኞች ከከባቢ አየር ውስጥ ከፍተኛ መጠን ያለው በካይ ጋዝ የመምጠጥ እና የማከማቸት አቅም ስላላቸው ለኢትዮጵያ አዲስ እና ዘላቂ የዶላር መገኛ መስመር እየከፈቱም ይገኛሉ።
መርሐ ግብሩ ከሀገራዊ ፋይዳው ባሻገር የኢትዮጵያን ስልታዊ የውጭ ፖሊሲ እና ቀጣናዊ ትስስር የሚያጠናክር የአረንጓዴ ዲፕሎማሲ መሳሪያ ሆኗል።
ኢትዮጵያ ለጎረቤት ሀገራት ለጂቡቲ፣ ለኬንያ፣ ለሶማሊያ እና ለደቡብ ሱዳን በሚሊየን የሚቆጠሩ ችግኞችን በነጻ በማካፈል በጋራ የመልማትና ድንበር ተሻጋሪ የተፈጥሮ ሀብትን በጋራ የመጠበቅ ራዕይን በተግባር አሳይታለች።
የኢትዮጵያ አረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር ዛፍ ከመትከል በእጅጉ የላቀ፣ ሀገራዊ ብልጽግናን ከዓለም አቀፍ ዲፕሎማሲ ጋር ያስተሳሰረ ታላቅ ስትራቴጂካዊ ርምጃ ነው። ይህ ንቅናቄ ለተተኪው ትውልድ የሚለምልም እና የሚጠቅም ሕያው ቅርስ እና የማያረጅ ውርስ ጥሎ የሚያልፍ የአዲሱ አረንጓዴ ኢኮኖሚ ግንባታ ማሳያ ነው።
የአረንጓዴ ዐሻራ ንቅናቄው ኢትዮጵያን በአፍሪካና በዓለም አቀፍ መድረክ የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ተምሳሌት እያደረገም ይገኛል።
በወንድማገኝ ጸጋዬ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 9፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የአረንጓዴ ዐሻራ ሀገራዊ ንቅናቄ የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት ከማረጋገጥ እና ብልጽግናን ከማምጣት የረጅም ጊዜ ሀገራዊ ሕልም ጋር በቀጥታ የተቆራኘ አንኳር ጉዳይ ነው።
የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር ኢትዮጵያን በዓለም አቀፍ ደረጃ አርዓያ ያደረገ እና የምትታወቅበት መገለጫ ሆኗል፡፡
መርሐ ግብሩ የተመጣጠነ ዝናብ እንዲኖር፣ ከተፈጥሮ ጋር ተስማምቶ ለመኖር እና በምግብ ራስን ለመቻል ትልቅ እገዛ እያደረገም ይገኛል፡፡
ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የአረንጓዴ ዐሻራ ተግባራት እንደ ሀገር በተጨባጭ የደን መመናመንን በማስቀረት ሽፋኑን ማሳደግ ተችሏል፡፡
ለካርበን ሽያጭና ዛፍ መትከል ስለሚያስገኘው የቢሊየን ዶላሮች የኢኮኖሚ ምንጭ ማወቅ የአሁኑ ዘመን የሕልውና እና የብልጽግና መሠረትን ለመረዳት ወሳኝ መነሻ ነው።
አረንጓዴ ዐሻራ የዓለም አቀፉን የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖ ከመቋቋም ባለፈ ታላቅ ሀገራዊና አሕጉራዊ ፋይዳ ያለው ሲሆን÷ ይህ ታሪካዊ መርሐ ግብር ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ መድረክ ያላትን ተጽዕኖ ፈጣሪነት በማሳደግ አዲስ የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ምዕራፍ ከፍቷል፡፡
በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አነሳሽነት የተጀመረው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር ጊዜያዊ ዘመቻ ሳይሆን የሀገርን የነገ ዕጣ ፈንታ የሚወስን ሆኖ ቀጥሏል።
በዚህም ከፍተኛ የኢኮኖሚ ጠቀሜታ ያላቸውና የምግብ ዋስትናን በተግባር የሚያረጋግጡ የፍራፍሬ ዝርያዎችን ጨምሮ የተለያዩ ችግኞች በመተከላቸው የአርሶ አደሩን የኑሮ ደረጃ በከፍተኛ ሁኔታ እየቀየሩ ይገኛሉ።
ከተከላው ጎን ለጎን ችግኞችን በማፍላትና በመንከባከብ ሂደት ውስጥ ለሚሊየኖች ሰፊ የሥራ ዕድል ተፈጥሯል።
በአረንጓዴ ዐሻራ የሚተከሉ ችግኞች ከከባቢ አየር ውስጥ ከፍተኛ መጠን ያለው በካይ ጋዝ የመምጠጥ እና የማከማቸት አቅም ስላላቸው ለኢትዮጵያ አዲስ እና ዘላቂ የዶላር መገኛ መስመር እየከፈቱም ይገኛሉ።
መርሐ ግብሩ ከሀገራዊ ፋይዳው ባሻገር የኢትዮጵያን ስልታዊ የውጭ ፖሊሲ እና ቀጣናዊ ትስስር የሚያጠናክር የአረንጓዴ ዲፕሎማሲ መሳሪያ ሆኗል።
ኢትዮጵያ ለጎረቤት ሀገራት ለጂቡቲ፣ ለኬንያ፣ ለሶማሊያ እና ለደቡብ ሱዳን በሚሊየን የሚቆጠሩ ችግኞችን በነጻ በማካፈል በጋራ የመልማትና ድንበር ተሻጋሪ የተፈጥሮ ሀብትን በጋራ የመጠበቅ ራዕይን በተግባር አሳይታለች።
የኢትዮጵያ አረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር ዛፍ ከመትከል በእጅጉ የላቀ፣ ሀገራዊ ብልጽግናን ከዓለም አቀፍ ዲፕሎማሲ ጋር ያስተሳሰረ ታላቅ ስትራቴጂካዊ ርምጃ ነው። ይህ ንቅናቄ ለተተኪው ትውልድ የሚለምልም እና የሚጠቅም ሕያው ቅርስ እና የማያረጅ ውርስ ጥሎ የሚያልፍ የአዲሱ አረንጓዴ ኢኮኖሚ ግንባታ ማሳያ ነው።
የአረንጓዴ ዐሻራ ንቅናቄው ኢትዮጵያን በአፍሪካና በዓለም አቀፍ መድረክ የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ተምሳሌት እያደረገም ይገኛል።
በወንድማገኝ ጸጋዬ
2 months ago
የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በጁባ ዘመናዊ የመኖሪያና የንግድ ቤቶች ግንባታ ለመጀመር የመጨረሻ ዝግጅቱን አጠናቀቀ
የኢትዮጵያ ፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በደቡብ ሱዳን ዋና ከተማ ጁባ ዘመናዊ የመኖሪያ እና የንግድ ተቋማት ግንባታን ለመጀመር የሚያስችሉትን ሁሉንም አስፈላጊ ቅድመ-ዝግጅቶች ማጠናቀቁንና ወደ ተግባር ለመግባት መዘጋጀቱን አስታወቀ።
ይህ ግዙፍ ፕሮጀክት ወደ ትግበራ ምዕራፍ የተሸጋገረው ባለፈዉ ቅዳሜ ዕለት በጁባ ከተማ በተፈረመው የመጨረሻ የኦፕሬሽን ውል መሠረት ሲሆን፣ ስምምነቱ ቀደም ሲል በሁለቱ ወገኖች መካከል በአዲስ አበባ ተፈርሞ የነበረውን የመግባቢያ ሰነድ በቀጥታ ወደ ሥራ የሚያስገባ ነው።
ስምምነቱን የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ረሻድ ከማል እና የደቡብ ሱዳን የመካከለኛው ኢኳቶሪያ ግዛት ገዥ ኢማኑኤል አዲል በጋራ ፈርመውታል። በዚህ ስትራቴጂካዊ አጋርነት መሠረት ኮርፖሬሽኑ በጁባ ከተማ በፍጥነት እያደገ የመጣውን የቤት ፍላጎት ለማሟላት የሚያስችሉ ዘመናዊ የንግድ ማዕከላትን እና የመኖሪያ ሕንፃዎችን ግንባታ በበላይነት ይመራል ተብሏል።
Via capital
የኢትዮጵያ ፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በደቡብ ሱዳን ዋና ከተማ ጁባ ዘመናዊ የመኖሪያ እና የንግድ ተቋማት ግንባታን ለመጀመር የሚያስችሉትን ሁሉንም አስፈላጊ ቅድመ-ዝግጅቶች ማጠናቀቁንና ወደ ተግባር ለመግባት መዘጋጀቱን አስታወቀ።
ይህ ግዙፍ ፕሮጀክት ወደ ትግበራ ምዕራፍ የተሸጋገረው ባለፈዉ ቅዳሜ ዕለት በጁባ ከተማ በተፈረመው የመጨረሻ የኦፕሬሽን ውል መሠረት ሲሆን፣ ስምምነቱ ቀደም ሲል በሁለቱ ወገኖች መካከል በአዲስ አበባ ተፈርሞ የነበረውን የመግባቢያ ሰነድ በቀጥታ ወደ ሥራ የሚያስገባ ነው።
ስምምነቱን የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ረሻድ ከማል እና የደቡብ ሱዳን የመካከለኛው ኢኳቶሪያ ግዛት ገዥ ኢማኑኤል አዲል በጋራ ፈርመውታል። በዚህ ስትራቴጂካዊ አጋርነት መሠረት ኮርፖሬሽኑ በጁባ ከተማ በፍጥነት እያደገ የመጣውን የቤት ፍላጎት ለማሟላት የሚያስችሉ ዘመናዊ የንግድ ማዕከላትን እና የመኖሪያ ሕንፃዎችን ግንባታ በበላይነት ይመራል ተብሏል።
Via capital
2 months ago
የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በጁባ
#ethiopia | የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በደቡብ ሱዳን ጁባ ከተማ ለሚያካሂደው ዘመናዊ የመኖሪያና የንግድ ቤቶች ግንባታ አስፈላጊው ቅድመ ዝግጅት መጠናቀቁን የደቡብ ሱዳን መንግሥት አስታውቋል።
ኮርፖሬሽኑ ግንባታውን ለማከናወን የሚያስችለውን ስምምነት የፈረመ ሲሆን፣ የህንጻ ግንባታ ቦታዎች መረጣ እና ተያያዥ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች አፈጻጸም በግዛቱ የኮንስትራክሽን እና ቤቶች ኮርፖሬሽን በቀረበ የጥናት ሪፖርት አማካኝነት በዝርዝር ተገምግሟል።
ቀደም ሲል በአዲስ አበባ ከተማ የተደረሰውን የመግባቢያ ስምምነት ወደ ተግባር የሚቀይረው ይኸው አዲስ ውል በጁባ ከተማ ተፈርሟል።
ስምምነቱን የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን ዋና ሥራ አስፈጻሚ ዶክተር ረሻድ ከማል እና የደቡብ ሱዳን ሴንተራል ኢኳቶሪያል ግዛት አስተዳዳሪ ክቡር ኢማኑኤል አድል ተፈራርመውታል። በዚህም መሠረት ኮርፖሬሽኑ በጁባ ከተማ ዘመናዊ የንግድና የመኖሪያ ሕንጻዎችን የሚገነባ ይሆናል።
ከዚሁ ጋር ተያይዞ የኮርፖሬሽኑ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ዶክተር ረሻድ ከማል ከደቡብ ሱዳን መንግሥት ልዩ መልዕክተኛ ክብርት አዱት ኪር ጋር ውጤታማ ውይይት አካሂደዋል።
በውይይቱ መድረክ ላይ በደቡብ ሱዳን የኢትዮጵያ አምባሳደር ክቡር ደሊል ከድር እና በደቡብ ሱዳን በተለያዩ የኢንቨስትመንት ዘርፎች የተሰማሩት ታዋቂው ባለሀብት ዶክተር አይሸሽም ተካ ተገኝተዋል።
በመድረኩ ላይ ክብርት አዱት ኪር ኮርፖሬሽኑ በጁባ ከተማ ለሚያካሂደው የቤት ልማት ፕሮግራም የደቡብ ሱዳን ፌዴራል መንግሥት አስፈላጊውን ድጋፍ ሁሉ እንደሚያደርግ አጽንኦት ሰጥተው ገልጸዋል።
ይህ የቤት ግንባታ መጀመር በሁለቱ እህትማማች አገራት መካከል ያለውን ጠንካራና ታሪካዊ ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ እንደሚያሸጋግረው ያላቸውን ሙሉ እምነት በመግለጽ፣ የደቡብ ሱዳን መንግሥት ለስምምነቱ ተግባራዊነት ያለውን ቁርጠኝነት አረጋግጠዋል።
ዋና ሥራ አስፈጻሚው ዶክተር ረሻድ ከማል በበኩላቸው፣ የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በደቡብ ሱዳን የቤት ልማት ዘርፍ የተሰማራው የጋራ ተጠቃሚነትን፣ አብሮነትን እና ወንድማማችነትን መርህ አድርጎ መሆኑን ገልጸው፣ በአጭር ጊዜ ውስጥ ሙሉ በሙሉ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎችን አጠናቆ ግንባታው በይፋ እንደሚጀመር አስታውቀዋል።
የኮርፖሬሽኑ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ዶክተር ረሻድ ከማል እና በርሳቸው የሚመራው የሥራ ልዑካን ቡድን ለአራት ቀናት ሲያካሂድ የነበረውን ጉብኝት አጠናቆ ወደ አዲስ አበባ ተመልሷል።
#የፌዴራልቤቶችኮርፖሬሽን #ኢትዮጵያ #ደቡብሱዳን #ጁባ #ቤትልማት #ኮንስትራክሽን #ኢንቨስትመንት #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በደቡብ ሱዳን ጁባ ከተማ ለሚያካሂደው ዘመናዊ የመኖሪያና የንግድ ቤቶች ግንባታ አስፈላጊው ቅድመ ዝግጅት መጠናቀቁን የደቡብ ሱዳን መንግሥት አስታውቋል።
ኮርፖሬሽኑ ግንባታውን ለማከናወን የሚያስችለውን ስምምነት የፈረመ ሲሆን፣ የህንጻ ግንባታ ቦታዎች መረጣ እና ተያያዥ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች አፈጻጸም በግዛቱ የኮንስትራክሽን እና ቤቶች ኮርፖሬሽን በቀረበ የጥናት ሪፖርት አማካኝነት በዝርዝር ተገምግሟል።
ቀደም ሲል በአዲስ አበባ ከተማ የተደረሰውን የመግባቢያ ስምምነት ወደ ተግባር የሚቀይረው ይኸው አዲስ ውል በጁባ ከተማ ተፈርሟል።
ስምምነቱን የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን ዋና ሥራ አስፈጻሚ ዶክተር ረሻድ ከማል እና የደቡብ ሱዳን ሴንተራል ኢኳቶሪያል ግዛት አስተዳዳሪ ክቡር ኢማኑኤል አድል ተፈራርመውታል። በዚህም መሠረት ኮርፖሬሽኑ በጁባ ከተማ ዘመናዊ የንግድና የመኖሪያ ሕንጻዎችን የሚገነባ ይሆናል።
ከዚሁ ጋር ተያይዞ የኮርፖሬሽኑ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ዶክተር ረሻድ ከማል ከደቡብ ሱዳን መንግሥት ልዩ መልዕክተኛ ክብርት አዱት ኪር ጋር ውጤታማ ውይይት አካሂደዋል።
በውይይቱ መድረክ ላይ በደቡብ ሱዳን የኢትዮጵያ አምባሳደር ክቡር ደሊል ከድር እና በደቡብ ሱዳን በተለያዩ የኢንቨስትመንት ዘርፎች የተሰማሩት ታዋቂው ባለሀብት ዶክተር አይሸሽም ተካ ተገኝተዋል።
በመድረኩ ላይ ክብርት አዱት ኪር ኮርፖሬሽኑ በጁባ ከተማ ለሚያካሂደው የቤት ልማት ፕሮግራም የደቡብ ሱዳን ፌዴራል መንግሥት አስፈላጊውን ድጋፍ ሁሉ እንደሚያደርግ አጽንኦት ሰጥተው ገልጸዋል።
ይህ የቤት ግንባታ መጀመር በሁለቱ እህትማማች አገራት መካከል ያለውን ጠንካራና ታሪካዊ ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ እንደሚያሸጋግረው ያላቸውን ሙሉ እምነት በመግለጽ፣ የደቡብ ሱዳን መንግሥት ለስምምነቱ ተግባራዊነት ያለውን ቁርጠኝነት አረጋግጠዋል።
ዋና ሥራ አስፈጻሚው ዶክተር ረሻድ ከማል በበኩላቸው፣ የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በደቡብ ሱዳን የቤት ልማት ዘርፍ የተሰማራው የጋራ ተጠቃሚነትን፣ አብሮነትን እና ወንድማማችነትን መርህ አድርጎ መሆኑን ገልጸው፣ በአጭር ጊዜ ውስጥ ሙሉ በሙሉ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎችን አጠናቆ ግንባታው በይፋ እንደሚጀመር አስታውቀዋል።
የኮርፖሬሽኑ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ዶክተር ረሻድ ከማል እና በርሳቸው የሚመራው የሥራ ልዑካን ቡድን ለአራት ቀናት ሲያካሂድ የነበረውን ጉብኝት አጠናቆ ወደ አዲስ አበባ ተመልሷል።
#የፌዴራልቤቶችኮርፖሬሽን #ኢትዮጵያ #ደቡብሱዳን #ጁባ #ቤትልማት #ኮንስትራክሽን #ኢንቨስትመንት #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
Sponsored by
Surafel
2 months ago
ደቡብ ሱዳን ከኢትዮጵያ ወሰን አቅራቢያ የሚገኘውን የግብፅ የጦር ሰፈር እንዲዘጋ አደረገች
#ethiopia | ደቡብ ሱዳን ከኢትዮጵያ ድንበር ጋር በሚገናኘው የበላይኛው ናይል ክፍለ ሀገር ፓጋክ በተባለ ስፍራ ሲንቀሳቀስ የነበረውን የግብፅ ወታደራዊ ማዕከል እንዲዘጋ ወስነች።
ይህ የጦር ሰፈር ግብፅ ታላቁ የህዳሴ ግድብን በተመለከተ ያላትን ጥቅምና ፍላጎት ለመጠበቅ ስትጠቀምበት የነበረ ስትራቴጂያዊ የክትትል ቦታ እንደነበር ተመልክቷል።
ይህ የጁባ ውሳኔ በቀጠናው የፖለቲካና የኃይል ሚዛን ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ እንደሚያሳድር የገለጹት የፖለቲካ ምሁራን፣ ደቡብ ሱዳን በሱዳን ጦርነት ምክንያት የተስተጓጎለባትን የነዳጅ ንግድ ለመተካት ከኢትዮጵያ ጋር የጀመረችውን የኢኮኖሚና የመሠረተ ልማት ትስስር ይበልጥ ለማሳደግ የያዘችውን አቋም የሚያሳይ ነው ብለዋል።
በፓጋክ ይንቀሳቀስ በነበረው በዚህ የግብፅ ወታደራዊ ጣቢያ ውስጥ የቴክኒክና የሎጂስቲክስ ባለሙያዎችን ጨምሮ ወደ 260 የሚጠጉ የግብፅ ዜጎች ይገኙበት እንደነበር ተገልጿል።
ባለፉት ሳምንታት በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለው ግንኙነት መሻከር አሳይቶ የነበረ ሲሆን፣ የደቡብ ሱዳን የአሁኑ እርምጃ በምስራቅ አፍሪካ የፖለቲካ አሰላለፍ ላይ ትልቅ መነጋገሪያ አጀንዳ ሆኗል።
#southsudan #egypt #gerd #grandethiopianrenaissancedam #pagak #eastafrica #politics #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | ደቡብ ሱዳን ከኢትዮጵያ ድንበር ጋር በሚገናኘው የበላይኛው ናይል ክፍለ ሀገር ፓጋክ በተባለ ስፍራ ሲንቀሳቀስ የነበረውን የግብፅ ወታደራዊ ማዕከል እንዲዘጋ ወስነች።
ይህ የጦር ሰፈር ግብፅ ታላቁ የህዳሴ ግድብን በተመለከተ ያላትን ጥቅምና ፍላጎት ለመጠበቅ ስትጠቀምበት የነበረ ስትራቴጂያዊ የክትትል ቦታ እንደነበር ተመልክቷል።
ይህ የጁባ ውሳኔ በቀጠናው የፖለቲካና የኃይል ሚዛን ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ እንደሚያሳድር የገለጹት የፖለቲካ ምሁራን፣ ደቡብ ሱዳን በሱዳን ጦርነት ምክንያት የተስተጓጎለባትን የነዳጅ ንግድ ለመተካት ከኢትዮጵያ ጋር የጀመረችውን የኢኮኖሚና የመሠረተ ልማት ትስስር ይበልጥ ለማሳደግ የያዘችውን አቋም የሚያሳይ ነው ብለዋል።
በፓጋክ ይንቀሳቀስ በነበረው በዚህ የግብፅ ወታደራዊ ጣቢያ ውስጥ የቴክኒክና የሎጂስቲክስ ባለሙያዎችን ጨምሮ ወደ 260 የሚጠጉ የግብፅ ዜጎች ይገኙበት እንደነበር ተገልጿል።
ባለፉት ሳምንታት በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለው ግንኙነት መሻከር አሳይቶ የነበረ ሲሆን፣ የደቡብ ሱዳን የአሁኑ እርምጃ በምስራቅ አፍሪካ የፖለቲካ አሰላለፍ ላይ ትልቅ መነጋገሪያ አጀንዳ ሆኗል።
#southsudan #egypt #gerd #grandethiopianrenaissancedam #pagak #eastafrica #politics #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
2 months ago
ደቡብ ሱዳን ከኢትዮጵያ ወሰን አቅራቢያ የሚገኘውን የግብፅ የጦር ሰፈር እንዲዘጋ አደረገች
#ethiopia | ደቡብ ሱዳን ከኢትዮጵያ ድንበር ጋር በሚገናኘው የበላይኛው ናይል ክፍለ ሀገር ፓጋክ በተባለ ስፍራ ሲንቀሳቀስ የነበረውን የግብፅ ወታደራዊ ማዕከል እንዲዘጋ ወስነች።
ይህ የጦር ሰፈር ግብፅ ታላቁ የህዳሴ ግድብን በተመለከተ ያላትን ጥቅምና ፍላጎት ለመጠበቅ ስትጠቀምበት የነበረ ስትራቴጂያዊ የክትትል ቦታ እንደነበር ተመልክቷል።
ይህ የጁባ ውሳኔ በቀጠናው የፖለቲካና የኃይል ሚዛን ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ እንደሚያሳድር የገለጹት የፖለቲካ ምሁራን፣ ደቡብ ሱዳን በሱዳን ጦርነት ምክንያት የተስተጓጎለባትን የነዳጅ ንግድ ለመተካት ከኢትዮጵያ ጋር የጀመረችውን የኢኮኖሚና የመሠረተ ልማት ትስስር ይበልጥ ለማሳደግ የያዘችውን አቋም የሚያሳይ ነው ብለዋል።
በፓጋክ ይንቀሳቀስ በነበረው በዚህ የግብፅ ወታደራዊ ጣቢያ ውስጥ የቴክኒክና የሎጂስቲክስ ባለሙያዎችን ጨምሮ ወደ 260 የሚጠጉ የግብፅ ዜጎች ይገኙበት እንደነበር ተገልጿል።
ባለፉት ሳምንታት በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለው ግንኙነት መሻከር አሳይቶ የነበረ ሲሆን፣ የደቡብ ሱዳን የአሁኑ እርምጃ በምስራቅ አፍሪካ የፖለቲካ አሰላለፍ ላይ ትልቅ መነጋገሪያ አጀንዳ ሆኗል።
#southsudan #egypt #gerd #grandethiopianrenaissancedam #pagak #eastafrica #politics #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | ደቡብ ሱዳን ከኢትዮጵያ ድንበር ጋር በሚገናኘው የበላይኛው ናይል ክፍለ ሀገር ፓጋክ በተባለ ስፍራ ሲንቀሳቀስ የነበረውን የግብፅ ወታደራዊ ማዕከል እንዲዘጋ ወስነች።
ይህ የጦር ሰፈር ግብፅ ታላቁ የህዳሴ ግድብን በተመለከተ ያላትን ጥቅምና ፍላጎት ለመጠበቅ ስትጠቀምበት የነበረ ስትራቴጂያዊ የክትትል ቦታ እንደነበር ተመልክቷል።
ይህ የጁባ ውሳኔ በቀጠናው የፖለቲካና የኃይል ሚዛን ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ እንደሚያሳድር የገለጹት የፖለቲካ ምሁራን፣ ደቡብ ሱዳን በሱዳን ጦርነት ምክንያት የተስተጓጎለባትን የነዳጅ ንግድ ለመተካት ከኢትዮጵያ ጋር የጀመረችውን የኢኮኖሚና የመሠረተ ልማት ትስስር ይበልጥ ለማሳደግ የያዘችውን አቋም የሚያሳይ ነው ብለዋል።
በፓጋክ ይንቀሳቀስ በነበረው በዚህ የግብፅ ወታደራዊ ጣቢያ ውስጥ የቴክኒክና የሎጂስቲክስ ባለሙያዎችን ጨምሮ ወደ 260 የሚጠጉ የግብፅ ዜጎች ይገኙበት እንደነበር ተገልጿል።
ባለፉት ሳምንታት በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለው ግንኙነት መሻከር አሳይቶ የነበረ ሲሆን፣ የደቡብ ሱዳን የአሁኑ እርምጃ በምስራቅ አፍሪካ የፖለቲካ አሰላለፍ ላይ ትልቅ መነጋገሪያ አጀንዳ ሆኗል።
#southsudan #egypt #gerd #grandethiopianrenaissancedam #pagak #eastafrica #politics #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
2 months ago
የእንግሊዝ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በተለያዩ የኢትዮጵያ ክልሎች ላይ የጣለውን ጥብቅ የጉዞ እገዳ አደሰ
የእንግሊዝ የውጭ ጉዳይ ኮመንዌልዝ እና ልማት ቢሮ (FCDO) በኢትዮጵያ በተለያዩ አካባቢዎች ያለውን የፀጥታ ስጋት ተከትሎ ለዜጎቹ ያወጣውን ጥብቅ የጉዞ ማማከርያ መመሪያ አድሷል ሚኒስቴሩ በሀገሪቱ ስር የሰደደ አለመረጋጋት እና ግጭቶች ባሉባቸው በርካታ ክልሎችና የድንበር ቀጠናዎች ላይ "በፍጹም ጉዞ እንዳይደረግ" የሚለውን ቀጣይነት ያለው እገዳ በድጋሚ አሳስቧል።
1. ሙሉ በሙሉ ጉዞ የተከለከለባቸው የሀገሪቱ ክፍሎች (All Travel)
የእንግሊዝ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ባወጣው ወቅታዊ መመሪያ መሰረት በከፍተኛ የፀጥታ ስጋት ምክንያት በሦስት ዋና ዋና ክልሎች ማለትም በትግራይ በአማራ እና በጋምቤላ ክልሎች ላይ ሙሉ በሙሉ የጉዞ ክልከላ ጥሏል።
ከእነዚህም በተጨማሪ በተለያዩ የሀገሪቱ የድንበር ቀጠናዎች ላይ ጥብቅ እገዳዎች ተጥለዋል፦
የሱዳን ድንበር፦ከድንበሩ በ20 ኪ.ሜ ክልል ውስጥ (ቤኒሻንጉል-ጉሙዝ መተከል እና ማኦ ኮሞ ልዩ ዞንን ጨምሮ)
የደቡብ ሱዳን እና የኬንያ ድንበሮች፦ከድንበሩ በ10 ኪ.ሜ ክልል ውስጥ (የቱርካና ሃይቅ ዳርቻዎችን ጨምሮ)
የሶማሊያ ድንበር (በሶማሌ ክልል)
ከድንበሩ በ100 ኪ.ሜ ርቀት ውስጥ (ከጅጅጋ-ወጃሌ ዋና መንገድ እና ከወጃሌ መሻገሪያ ውጭ) በፍጹም ጉዞ እንዳይደረግ አሳስቧል።
በኦሮሚያ ክልልም ምዕራብ ወለጋ፣ ምስራቅ ወለጋ፣ ቄለም ወለጋ እና ሆሮ ጉድሩ ወለጋን ጨምሮ በምዕራብ ሸዋ እና ሰሜን ሸዋ የሚገኙ አካባቢዎች በዚሁ የ"በፍጹም ጉዞ አታድርጉ" ቀጠና ውስጥ ተካትተዋል።
2. "አስገዳጅ ካልሆነ በስተቀር" ጉዞ እንዳይደረግባቸው የተመከሩ አካባቢዎች (All but Essential)
የኤርትራ ድንበርን ተከትለው በሚገኙ ከ10 እስከ 15 ኪ.ሜ ርቀቶች ላይ በአብዛኛው የኦሮሚያ ምስራቅ ሸዋ ዞን (ከአዲስ አበባ-አዳማ የፍጥነት መንገድ እና ወደ ሐዋሳ ከሚወስደው መንገድ ውጭ) እንዲሁም በሶማሌ ክልል የሚገኙት ሲቲ፣ ኖጎብ፣ ጃራር፣ ሻቤሌ፣ ቆራሄ እና ዶሎ ዞኖች ተጓዦች በጣም አስገዳጅ ጉዳይ ካልገጠማቸው በስተቀር መሄድ እንደሌለባቸው ተገልጿል።
ሚኒስቴሩ አያይዞ እንዳሳወቀው በአዲስ አበባ የሚገኘው የእንግሊዝ ኤምባሲ ሰራተኞች የጉዞ እገዳ በተጣለባቸው በእነዚህ የሀገሪቱ ክፍሎች ተገኝተው ለዜጎቻቸው በአካል ምንም ዓይነት የቆንስላ ድጋፍ ማድረግ አይችሉም።
ይሁን እንጂ ዜጎቻቸው በቁጥጥር ስር መዋልን የመሰሉ ከባድ ድንገተኛ አደጋዎች ሲገጥሟቸው በአዲስ አበባ በሚገኘው ዋናው ኤምባሲ በኩል በስልክ ጥሪ ማድረግ እንደሚችሉ ተገልጿል።
ተጓዦች ወደ ሀገሪቱ ከመንቀሳቀሳቸው በፊት ሙሉ የጉዞ ዋስትና (Travel Insurance) ሊኖራቸው እንደሚገባም መመሪያው አሳስቧል።
የእንግሊዝ የውጭ ጉዳይ ኮመንዌልዝ እና ልማት ቢሮ (FCDO) በኢትዮጵያ በተለያዩ አካባቢዎች ያለውን የፀጥታ ስጋት ተከትሎ ለዜጎቹ ያወጣውን ጥብቅ የጉዞ ማማከርያ መመሪያ አድሷል ሚኒስቴሩ በሀገሪቱ ስር የሰደደ አለመረጋጋት እና ግጭቶች ባሉባቸው በርካታ ክልሎችና የድንበር ቀጠናዎች ላይ "በፍጹም ጉዞ እንዳይደረግ" የሚለውን ቀጣይነት ያለው እገዳ በድጋሚ አሳስቧል።
1. ሙሉ በሙሉ ጉዞ የተከለከለባቸው የሀገሪቱ ክፍሎች (All Travel)
የእንግሊዝ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ባወጣው ወቅታዊ መመሪያ መሰረት በከፍተኛ የፀጥታ ስጋት ምክንያት በሦስት ዋና ዋና ክልሎች ማለትም በትግራይ በአማራ እና በጋምቤላ ክልሎች ላይ ሙሉ በሙሉ የጉዞ ክልከላ ጥሏል።
ከእነዚህም በተጨማሪ በተለያዩ የሀገሪቱ የድንበር ቀጠናዎች ላይ ጥብቅ እገዳዎች ተጥለዋል፦
የሱዳን ድንበር፦ከድንበሩ በ20 ኪ.ሜ ክልል ውስጥ (ቤኒሻንጉል-ጉሙዝ መተከል እና ማኦ ኮሞ ልዩ ዞንን ጨምሮ)
የደቡብ ሱዳን እና የኬንያ ድንበሮች፦ከድንበሩ በ10 ኪ.ሜ ክልል ውስጥ (የቱርካና ሃይቅ ዳርቻዎችን ጨምሮ)
የሶማሊያ ድንበር (በሶማሌ ክልል)
ከድንበሩ በ100 ኪ.ሜ ርቀት ውስጥ (ከጅጅጋ-ወጃሌ ዋና መንገድ እና ከወጃሌ መሻገሪያ ውጭ) በፍጹም ጉዞ እንዳይደረግ አሳስቧል።
በኦሮሚያ ክልልም ምዕራብ ወለጋ፣ ምስራቅ ወለጋ፣ ቄለም ወለጋ እና ሆሮ ጉድሩ ወለጋን ጨምሮ በምዕራብ ሸዋ እና ሰሜን ሸዋ የሚገኙ አካባቢዎች በዚሁ የ"በፍጹም ጉዞ አታድርጉ" ቀጠና ውስጥ ተካትተዋል።
2. "አስገዳጅ ካልሆነ በስተቀር" ጉዞ እንዳይደረግባቸው የተመከሩ አካባቢዎች (All but Essential)
የኤርትራ ድንበርን ተከትለው በሚገኙ ከ10 እስከ 15 ኪ.ሜ ርቀቶች ላይ በአብዛኛው የኦሮሚያ ምስራቅ ሸዋ ዞን (ከአዲስ አበባ-አዳማ የፍጥነት መንገድ እና ወደ ሐዋሳ ከሚወስደው መንገድ ውጭ) እንዲሁም በሶማሌ ክልል የሚገኙት ሲቲ፣ ኖጎብ፣ ጃራር፣ ሻቤሌ፣ ቆራሄ እና ዶሎ ዞኖች ተጓዦች በጣም አስገዳጅ ጉዳይ ካልገጠማቸው በስተቀር መሄድ እንደሌለባቸው ተገልጿል።
ሚኒስቴሩ አያይዞ እንዳሳወቀው በአዲስ አበባ የሚገኘው የእንግሊዝ ኤምባሲ ሰራተኞች የጉዞ እገዳ በተጣለባቸው በእነዚህ የሀገሪቱ ክፍሎች ተገኝተው ለዜጎቻቸው በአካል ምንም ዓይነት የቆንስላ ድጋፍ ማድረግ አይችሉም።
ይሁን እንጂ ዜጎቻቸው በቁጥጥር ስር መዋልን የመሰሉ ከባድ ድንገተኛ አደጋዎች ሲገጥሟቸው በአዲስ አበባ በሚገኘው ዋናው ኤምባሲ በኩል በስልክ ጥሪ ማድረግ እንደሚችሉ ተገልጿል።
ተጓዦች ወደ ሀገሪቱ ከመንቀሳቀሳቸው በፊት ሙሉ የጉዞ ዋስትና (Travel Insurance) ሊኖራቸው እንደሚገባም መመሪያው አሳስቧል።
2 months ago
የኢቦላ ስጋት እና የሀገራት ጥንቃቄ
የተባበሩት አረብ ኤምሬትስን (UAE) ጨምሮ በርካታ ሀገራት የኢቦላ ቫይረስ ወደ ሀገራቸው እንዳይገባ ጠንካራ የጥንቃቄ እርምጃዎችን መውሰድ ጀምረዋል።
በዚህም መሰረት ሦስት ሀገራት ዜጎች ከዛሬ ጀምሮ ለጊዜው ወደ ሀገራቸው እንዳይገቡ እገዳ ጥለዋል።
እነዚህ ሀገራትም፦
* ዲ.አር. ኮንጎ (DRC)
* ደቡብ ሱዳን እና
* ኡጋንዳ ናቸው።
Via GN
በአየር ትራንስፖርት ዘርፍ የአፍሪካ መገናኛ ማዕከል እንደመሆናችን መጠን፣ የኢትዮጵያ መንግስት እና የሚመለከታቸው የጤና ተቋማት ይህንን ወቅታዊ ሁኔታ በአስቸኳይ አይተው፣ የህዝባችንን ደህንነት ለመጠበቅ ሲባል አፋጣኝ ውሳኔና የጥንቃቄ እርምጃ ቢወስዱበት መልካም ነው እንላለን።
ጤና ለሀገራችን! 🇪🇹
Seledadotio
Seledadotio
የተባበሩት አረብ ኤምሬትስን (UAE) ጨምሮ በርካታ ሀገራት የኢቦላ ቫይረስ ወደ ሀገራቸው እንዳይገባ ጠንካራ የጥንቃቄ እርምጃዎችን መውሰድ ጀምረዋል።
በዚህም መሰረት ሦስት ሀገራት ዜጎች ከዛሬ ጀምሮ ለጊዜው ወደ ሀገራቸው እንዳይገቡ እገዳ ጥለዋል።
እነዚህ ሀገራትም፦
* ዲ.አር. ኮንጎ (DRC)
* ደቡብ ሱዳን እና
* ኡጋንዳ ናቸው።
Via GN
በአየር ትራንስፖርት ዘርፍ የአፍሪካ መገናኛ ማዕከል እንደመሆናችን መጠን፣ የኢትዮጵያ መንግስት እና የሚመለከታቸው የጤና ተቋማት ይህንን ወቅታዊ ሁኔታ በአስቸኳይ አይተው፣ የህዝባችንን ደህንነት ለመጠበቅ ሲባል አፋጣኝ ውሳኔና የጥንቃቄ እርምጃ ቢወስዱበት መልካም ነው እንላለን።
ጤና ለሀገራችን! 🇪🇹
Seledadotio
Seledadotio
2 months ago
ደቡብ ሱዳን በድንበሯ ላይ የተገነባውን
የግብፅ ጦር ሠፈር እንዲዘጋ አዘዘች
የደቡብ ሱዳን መንግሥት፣ ግብፅ በኢትዮጵያ ድንበር አቅራቢያ በሚገኘው የላይኛው ናይል ግዛት ፓጋክ አካባቢ ያቋቋመችውን ወታደራዊ ጦር ሠፈር በአስቸኳይ እንድትዘጋ ማዘዙን የዓረብኛ የዜና ምንጮች በሰፊው ዘግበዋል።
ይህ በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል አቅራቢያ የተገነባውና ወታደራዊ ሥልጠና የመስጠት እንዲሁም የናይል ወንዝ ፍሰትን የመቆጣጠር ስውር ዓላማ የነበረው ጦር ሠፈር፣ የሥልጠና ባለሙያዎችን ጨምሮ 260 የሚያህል የሰው ኃይል አሰማርቶ የነበረ መሆኑ ታውቋል።
Seledadotio
Seledadotio
የግብፅ ጦር ሠፈር እንዲዘጋ አዘዘች
የደቡብ ሱዳን መንግሥት፣ ግብፅ በኢትዮጵያ ድንበር አቅራቢያ በሚገኘው የላይኛው ናይል ግዛት ፓጋክ አካባቢ ያቋቋመችውን ወታደራዊ ጦር ሠፈር በአስቸኳይ እንድትዘጋ ማዘዙን የዓረብኛ የዜና ምንጮች በሰፊው ዘግበዋል።
ይህ በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል አቅራቢያ የተገነባውና ወታደራዊ ሥልጠና የመስጠት እንዲሁም የናይል ወንዝ ፍሰትን የመቆጣጠር ስውር ዓላማ የነበረው ጦር ሠፈር፣ የሥልጠና ባለሙያዎችን ጨምሮ 260 የሚያህል የሰው ኃይል አሰማርቶ የነበረ መሆኑ ታውቋል።
Seledadotio
Seledadotio
2 months ago
2 months ago
ኢትዮጵያን ጨምሮ አስር አገራት በኢቦላ ቫይረስ የመጠቃት ስጋት አላቸው‼️
የአፍሪካ ህብረት የጤና ኤጀንሲ ኢትዮጵያን ጨምሮ አስር አገራት በኢቦላ ቫይረስ የመጠቃት ስጋት እንዳለባቸዉ አስጠነቀቀ።
ኢትዮጵያን፣ ኬንያን፣ ሩዋንዳንና ደቡብ ሱዳንን ጨምሮ አስር ሀገራት በኢቦላ ቫይረስ የመጠቃት ስጋት እንዳለባቸው ህብረቱ አስጠንቅቋል፡፡
የዓለም ጤና ድርጅት በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ያለውን የኢቦላ ስጋት ወደ ከፍተኛው ደረጃ ከፍ ማድረጉን ተከትሎ፣ የአፍሪካ ህብረት ቫይረሱ 10 አገሮችን ሊያጠቃ እንደሚችል በማስጠንቀቅ ላይ ይገኛል።
ወረርሽኙ ለመጀመሪያ ጊዜ የተገኘው በኢቱሪ ግዛት ሲሆን፤ አካባቢው አስቀድሞም የትጥቅ ግጭቶችና ሰብዓዊ ቀውሶች የሚታዩበት ነው።
በቫይረሱ ከተያዙ ሰዎች ጋር ቀጥተኛ ወይም የቅርብ ንክኪን ማስወገድ የበሽታውን ስርጭት ለመቀነስና ወረርሽኙን ለመቆጣጠር ወሳኝ እርምጃ ነው።
እንደ ዓለም ጤና ድርጅት መረጃ ከሆነ፤ እስካሁን በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ 82 የተረጋገጡ ህመምተኞች እና ሰባት የሞቱ ሰዎች የተመዘገቡ ሲሆን፤ በተጨማሪም ወደ 7መቶ50 የሚጠጉ ኬዞች እና 1መቶ77 በኢቦላ ምክንያት ተከስተዋል ተብለዉ የተጠረጠሩ ሞቶች እንዳሉ ተገልጿል፡፡
በምስራቅ በኩል ከኮንጎ ጋር የምትዋሰነው ኡጋንዳ አምስት የኢቦላ ተጠቂዎችን አረጋግጣለች።
የአፍሪካ ህብረት የጤና ኤጀንሲ ትናንት ባወጣዉ መግለጫ፤ኢትዮጵያን፣ ኬንያን፣ ሩዋንዳንና ደቡብ ሱዳንን ጨምሮ አስር ሀገራት በኢቦላ ቫይረስ የመጠቃት ስጋት እንዳለባቸው አስጠንቅቋል።
Seledadotio
Seledadotio
የአፍሪካ ህብረት የጤና ኤጀንሲ ኢትዮጵያን ጨምሮ አስር አገራት በኢቦላ ቫይረስ የመጠቃት ስጋት እንዳለባቸዉ አስጠነቀቀ።
ኢትዮጵያን፣ ኬንያን፣ ሩዋንዳንና ደቡብ ሱዳንን ጨምሮ አስር ሀገራት በኢቦላ ቫይረስ የመጠቃት ስጋት እንዳለባቸው ህብረቱ አስጠንቅቋል፡፡
የዓለም ጤና ድርጅት በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ያለውን የኢቦላ ስጋት ወደ ከፍተኛው ደረጃ ከፍ ማድረጉን ተከትሎ፣ የአፍሪካ ህብረት ቫይረሱ 10 አገሮችን ሊያጠቃ እንደሚችል በማስጠንቀቅ ላይ ይገኛል።
ወረርሽኙ ለመጀመሪያ ጊዜ የተገኘው በኢቱሪ ግዛት ሲሆን፤ አካባቢው አስቀድሞም የትጥቅ ግጭቶችና ሰብዓዊ ቀውሶች የሚታዩበት ነው።
በቫይረሱ ከተያዙ ሰዎች ጋር ቀጥተኛ ወይም የቅርብ ንክኪን ማስወገድ የበሽታውን ስርጭት ለመቀነስና ወረርሽኙን ለመቆጣጠር ወሳኝ እርምጃ ነው።
እንደ ዓለም ጤና ድርጅት መረጃ ከሆነ፤ እስካሁን በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ 82 የተረጋገጡ ህመምተኞች እና ሰባት የሞቱ ሰዎች የተመዘገቡ ሲሆን፤ በተጨማሪም ወደ 7መቶ50 የሚጠጉ ኬዞች እና 1መቶ77 በኢቦላ ምክንያት ተከስተዋል ተብለዉ የተጠረጠሩ ሞቶች እንዳሉ ተገልጿል፡፡
በምስራቅ በኩል ከኮንጎ ጋር የምትዋሰነው ኡጋንዳ አምስት የኢቦላ ተጠቂዎችን አረጋግጣለች።
የአፍሪካ ህብረት የጤና ኤጀንሲ ትናንት ባወጣዉ መግለጫ፤ኢትዮጵያን፣ ኬንያን፣ ሩዋንዳንና ደቡብ ሱዳንን ጨምሮ አስር ሀገራት በኢቦላ ቫይረስ የመጠቃት ስጋት እንዳለባቸው አስጠንቅቋል።
Seledadotio
Seledadotio
Sponsored by
Surafel
2 months ago
የአፍሪካ ህብረት የጤና ኤጀንሲ ኢትዮጵያን ጨምሮ አስር አገራት በኢቦላ ቫይረስ የመጠቃት ስጋት እንዳለባቸዉ አስጠነቀቀ
ኢትዮጵያን፣ ኬንያን፣ ሩዋንዳንና ደቡብ ሱዳንን ጨምሮ አስር ሀገራት በኢቦላ ቫይረስ የመጠቃት ስጋት እንዳለባቸው ህብረቱ አስጠንቅቋል፡፡
የዓለም ጤና ድርጅት በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ያለውን የኢቦላ ስጋት ወደ ከፍተኛው ደረጃ ከፍ ማድረጉን ተከትሎ፣ የአፍሪካ ህብረት ቫይረሱ 10 አገሮችን ሊያጠቃ እንደሚችል በማስጠንቀቅ ላይ ይገኛል።
ወረርሽኙ ለመጀመሪያ ጊዜ የተገኘው በኢቱሪ ግዛት ሲሆን፤ አካባቢው አስቀድሞም የትጥቅ ግጭቶችና ሰብዓዊ ቀውሶች የሚታዩበት ነው።
በቫይረሱ ከተያዙ ሰዎች ጋር ቀጥተኛ ወይም የቅርብ ንክኪን ማስወገድ የበሽታውን ስርጭት ለመቀነስና ወረርሽኙን ለመቆጣጠር ወሳኝ እርምጃ ነው።
እንደ ዓለም ጤና ድርጅት መረጃ ከሆነ፤ እስካሁን በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ 82 የተረጋገጡ ህመምተኞች እና ሰባት የሞቱ ሰዎች የተመዘገቡ ሲሆን፤ በተጨማሪም ወደ 7መቶ50 የሚጠጉ ኬዞች እና 1መቶ77 በኢቦላ ምክንያት ተከስተዋል ተብለዉ የተጠረጠሩ ሞቶች እንዳሉ ተገልጿል፡፡
በምስራቅ በኩል ከኮንጎ ጋር የምትዋሰነው ኡጋንዳ አምስት የኢቦላ ተጠቂዎችን አረጋግጣለች።
የአፍሪካ ህብረት የጤና ኤጀንሲ ትናንት ባወጣዉ መግለጫ፤ኢትዮጵያን፣ ኬንያን፣ ሩዋንዳንና ደቡብ ሱዳንን ጨምሮ አስር ሀገራት በኢቦላ ቫይረስ የመጠቃት ስጋት እንዳለባቸው አስጠንቅቋል።
እስከዳር ግርማ
ኢትዮጵያን፣ ኬንያን፣ ሩዋንዳንና ደቡብ ሱዳንን ጨምሮ አስር ሀገራት በኢቦላ ቫይረስ የመጠቃት ስጋት እንዳለባቸው ህብረቱ አስጠንቅቋል፡፡
የዓለም ጤና ድርጅት በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ያለውን የኢቦላ ስጋት ወደ ከፍተኛው ደረጃ ከፍ ማድረጉን ተከትሎ፣ የአፍሪካ ህብረት ቫይረሱ 10 አገሮችን ሊያጠቃ እንደሚችል በማስጠንቀቅ ላይ ይገኛል።
ወረርሽኙ ለመጀመሪያ ጊዜ የተገኘው በኢቱሪ ግዛት ሲሆን፤ አካባቢው አስቀድሞም የትጥቅ ግጭቶችና ሰብዓዊ ቀውሶች የሚታዩበት ነው።
በቫይረሱ ከተያዙ ሰዎች ጋር ቀጥተኛ ወይም የቅርብ ንክኪን ማስወገድ የበሽታውን ስርጭት ለመቀነስና ወረርሽኙን ለመቆጣጠር ወሳኝ እርምጃ ነው።
እንደ ዓለም ጤና ድርጅት መረጃ ከሆነ፤ እስካሁን በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ 82 የተረጋገጡ ህመምተኞች እና ሰባት የሞቱ ሰዎች የተመዘገቡ ሲሆን፤ በተጨማሪም ወደ 7መቶ50 የሚጠጉ ኬዞች እና 1መቶ77 በኢቦላ ምክንያት ተከስተዋል ተብለዉ የተጠረጠሩ ሞቶች እንዳሉ ተገልጿል፡፡
በምስራቅ በኩል ከኮንጎ ጋር የምትዋሰነው ኡጋንዳ አምስት የኢቦላ ተጠቂዎችን አረጋግጣለች።
የአፍሪካ ህብረት የጤና ኤጀንሲ ትናንት ባወጣዉ መግለጫ፤ኢትዮጵያን፣ ኬንያን፣ ሩዋንዳንና ደቡብ ሱዳንን ጨምሮ አስር ሀገራት በኢቦላ ቫይረስ የመጠቃት ስጋት እንዳለባቸው አስጠንቅቋል።
እስከዳር ግርማ
Comments