50 mins. ago
ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ፡- በብዝኃነት ላይ የተመሠረተ ወል ትርክትን የመገንባት ጉዞ
*********************
ኢትዮጵያ በታሪኳ ትልቅ ምዕራፍ ላይ ትገኛለች። ሀገራችንን በጽኑ መሠረት ላይ ለመገንባት፣ ልዩነቶችን በሠለጠነ መንገድ ለመፍታት እና በዋና ዋና ብሔራዊ ጉዳዮች ላይ የጋራ መግባባት ለመፍጠር የተጀመረው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ የዚህ ዘመን ትልቁ ታሪካዊ ክስተት ነው።
እንደ ሀገር የገጠሙንን ዘመናት የተሻገሩ ፖለቲካዊ እና ማኅበራዊ ውጥንቅጦችን በዘላቂነት ለመፍታት ከግጭት ይልቅ ውይይትን፣ ከመግፋት ይልቅ አሳታፊነትን ማስቀደም ብቸኛው ዘላቂ መንገድ መሆኑ ግልጽ እውነታ ሆኗል።
የሀገራዊ ምክክሩ ዋነኛ ዓላማ በሕዝቦች መካከል ለዘመናት የዘለቁ እና መፍትሔ ያላገኙ መዋቅራዊ እና ፖለቲካዊ ልዩነቶችን ማጥበብ ነው። ሕዝቡ በነጻነት አስተያየቱን እንዲሰጥ በማድረግ የጋራ እሴቶችን መቅረጽ እንዲሁም ሀገራዊ አንድነትን እና ብዝኃነትን ያጣጣመ የጋራ የወደፊት ራዕይ በመቅረጽ የወል ትርክትን መገንባት ነው።
ይህንን የምክክር ሒደት ልዩ የሚያደርገው ከላይ ወደ ታች የሚወርድ ውሳኔ ሳይሆን፣ ከታች ወደ ላይ የኅብረተሰቡን ድምፅ የሚሰበስብ መሆኑ ነው። እውነተኛ ሀገር ግንባታ የሚጀምረውም የእያንዳንዱ ዜጋ ድምፅ እኩል ዋጋ አግኝቶ ሲደመጥ ብቻ ነው።
የተለያዩ የኅብረተሰብ ክፍሎች የሃይማኖት አባቶች፣ ወጣቶች፣ ሴቶች፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች እና የሲቪል ማኅበራት በተወካዮቻቸው አማካኝነት የአጀንዳ ግብዓት ማቅረባቸው የሒደቱን ተቀባይነት እና ሕጋዊነት በማጎልበት አሳታፊነትን ማረጋገጥ ተችሏል።
የሀገራዊ የምክክር ኮሚሽኑ በየክልሎቹ እና በከተማ አስተዳደሮች የአጀንዳ ማሰባሰብ እና የተወካዮች መረጣ ሒደቶችን ባከናወነበት ወቅት ሒደቱ ግልጽነት ያለው እና ገለልተኛ በሆነ መንገድ እንዲሄድ ማድረጉ ለምክክሩ ተዓማኒነት የራሱን ከፍተኛ አስተዋፅኦ አበርክቷል።
ሀገራዊ የምክክር ጉባኤው የትውልድ አደራ እና የጠንካራ ሀገር ግንባታ መሠረት ሲሆን፣ የዚህ ጉባኤ ስኬት የሚወሰነውም በኮሚሽኑ ጥረት ብቻ ሳይሆን በእያንዳንዳችን በጎ ፈቃድ፣ አዳምጦ የመረዳት ባህል እና ለሀገራዊ አንድነት በምናሳየው ቁርጠኝነት ነው።
ውጤታማ ምክክር ያደረጉ ሀገራት ከቀውስ ወጥተው ወደ ብልጽግና እንደተሸጋገሩ ሁሉ፣ ኢትዮጵያም በዚሁ መንገድ በሰላም፣ በእኩልነት እና በብልጽግና ላይ የተመሠረተች ሀገር ሆና እንደምትቀጥል እምነታችን የጸና ነው።
በአድማሱ አራጋው
#ethiopia #ebc #nationaldialogue #dialogue
*********************
ኢትዮጵያ በታሪኳ ትልቅ ምዕራፍ ላይ ትገኛለች። ሀገራችንን በጽኑ መሠረት ላይ ለመገንባት፣ ልዩነቶችን በሠለጠነ መንገድ ለመፍታት እና በዋና ዋና ብሔራዊ ጉዳዮች ላይ የጋራ መግባባት ለመፍጠር የተጀመረው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ የዚህ ዘመን ትልቁ ታሪካዊ ክስተት ነው።
እንደ ሀገር የገጠሙንን ዘመናት የተሻገሩ ፖለቲካዊ እና ማኅበራዊ ውጥንቅጦችን በዘላቂነት ለመፍታት ከግጭት ይልቅ ውይይትን፣ ከመግፋት ይልቅ አሳታፊነትን ማስቀደም ብቸኛው ዘላቂ መንገድ መሆኑ ግልጽ እውነታ ሆኗል።
የሀገራዊ ምክክሩ ዋነኛ ዓላማ በሕዝቦች መካከል ለዘመናት የዘለቁ እና መፍትሔ ያላገኙ መዋቅራዊ እና ፖለቲካዊ ልዩነቶችን ማጥበብ ነው። ሕዝቡ በነጻነት አስተያየቱን እንዲሰጥ በማድረግ የጋራ እሴቶችን መቅረጽ እንዲሁም ሀገራዊ አንድነትን እና ብዝኃነትን ያጣጣመ የጋራ የወደፊት ራዕይ በመቅረጽ የወል ትርክትን መገንባት ነው።
ይህንን የምክክር ሒደት ልዩ የሚያደርገው ከላይ ወደ ታች የሚወርድ ውሳኔ ሳይሆን፣ ከታች ወደ ላይ የኅብረተሰቡን ድምፅ የሚሰበስብ መሆኑ ነው። እውነተኛ ሀገር ግንባታ የሚጀምረውም የእያንዳንዱ ዜጋ ድምፅ እኩል ዋጋ አግኝቶ ሲደመጥ ብቻ ነው።
የተለያዩ የኅብረተሰብ ክፍሎች የሃይማኖት አባቶች፣ ወጣቶች፣ ሴቶች፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች እና የሲቪል ማኅበራት በተወካዮቻቸው አማካኝነት የአጀንዳ ግብዓት ማቅረባቸው የሒደቱን ተቀባይነት እና ሕጋዊነት በማጎልበት አሳታፊነትን ማረጋገጥ ተችሏል።
የሀገራዊ የምክክር ኮሚሽኑ በየክልሎቹ እና በከተማ አስተዳደሮች የአጀንዳ ማሰባሰብ እና የተወካዮች መረጣ ሒደቶችን ባከናወነበት ወቅት ሒደቱ ግልጽነት ያለው እና ገለልተኛ በሆነ መንገድ እንዲሄድ ማድረጉ ለምክክሩ ተዓማኒነት የራሱን ከፍተኛ አስተዋፅኦ አበርክቷል።
ሀገራዊ የምክክር ጉባኤው የትውልድ አደራ እና የጠንካራ ሀገር ግንባታ መሠረት ሲሆን፣ የዚህ ጉባኤ ስኬት የሚወሰነውም በኮሚሽኑ ጥረት ብቻ ሳይሆን በእያንዳንዳችን በጎ ፈቃድ፣ አዳምጦ የመረዳት ባህል እና ለሀገራዊ አንድነት በምናሳየው ቁርጠኝነት ነው።
ውጤታማ ምክክር ያደረጉ ሀገራት ከቀውስ ወጥተው ወደ ብልጽግና እንደተሸጋገሩ ሁሉ፣ ኢትዮጵያም በዚሁ መንገድ በሰላም፣ በእኩልነት እና በብልጽግና ላይ የተመሠረተች ሀገር ሆና እንደምትቀጥል እምነታችን የጸና ነው።
በአድማሱ አራጋው
#ethiopia #ebc #nationaldialogue #dialogue
9 hours ago
ኢትዮጵያ ለአካባቢ ጥበቃ ያላትን ቁርጠኝነት ለዓለም ያሳየችበት አረንጓዴ ዐሻራ
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 28፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር የግብርና ምርታማነትን ማሳደግን ጨምሮ ዘርፈ ብዙ ሀገራዊ ጠቀሜታዎችን እያበረከተ ነው፡፡
መርሐ ግብሩ የአካባቢ ጥበቃ ሚናውን በጥቂት ዓመታት ብቻ ከፍ አድርጓል፡፡ የአፈር መሸርሸርን በመከላከል እና የደን ሽፋንን በማሳደግ ረገድ ከፍተኛ ውጤት አሳይቷል።
ይህ ንቅናቄ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀሳብ አመንጪነት ከ2011 ዓ.ም ጀምሮ ሲተገበር ቆይቷል። በዚህም የዘንድሮውን ሳይጨምር ከ48 ቢሊየን በላይ ችግኞችን በመትከል ስኬት ተመዝግቦበታል።
የመላው ኢትዮጵያውያን ላብ ውጤት የሆነው አረንጓዴ ዐሻራ የአየር ንብረት ለውጥን እና የተፈጥሮ ሀብት መመናመንን ለመላቀቅ፣ ለምግብ ዋስትናና ለሥራ ዕድል ፈጠራ የተተለመ ትውልድ ተሻጋሪ እቅድ ነው።
የአየር ንብረት ለውጥ ተግዳሮትና የደን መመናመን የአፈር መሸርሸር እና የውሃ አካላት መድረቅ ፈተናዎችን አስከትሎ ነበር፡፡ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር በቁርጠኝነት መተግበሩ የደን መመናመንን በማስቀረት የአየር ንብረት ለውጥ ጫናን ለመቋቋም የሚያስችል አቅም ፈጥሯል።
በዚህም የአፈር መከላት ችግር ቀደም ሲል ከነበረው አንጻር በ50 በመቶ ያህል መቀነስ መቻሉ እና የውሃ አካላት በደለል የመሞላት ችግር መፈታቱ ዘርፈ ብዙ ጥቅም እየሰጠ ይገኛል።
ይህም የምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥ ባለፈ ፍራፍሬዎችን ጨምሮ የተለያዩ የግብርና ምርቶችን ወደ ውጭ የመላክ አቅሟን ለማሳደግ በቅታለች፡፡
የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር ህጻናትን፣ አዛውንቶችን፣ ወጣቶችን እና የመንግሥት ሰራተኞችን ጨምሮ መላውን ህዝብ አሳትፏል፡፡
መርሐ ግብሩ የተፈጥሮ ሀብትን ከመጠበቅ ባለፈ ሰፊ የስራ ዕድል ፈጥሯል።
የመላው ኢትዮጵያውያን የጋራ ላብ ውጤት የሆነው አረንጓዴ አሻራ ዛሬ ላይ የሚታይ ተጨባጭ የለምለም ተፈጥሮ መሠረት ብቻ ሳይሆን ለቀጣዩ ትውልድ ንጹህ አየር፣ ውሃ እና አፈርን የማስተላለፍ ዋስትና ነው።
ይህ ህዝባዊ ንቅናቄ ኢትዮጵያ ለአካባቢ ጥበቃ ያላትን ጽኑ ቁርጠኝነት ለዓለም ያስመሰከረችበት እና አረንጓዴ ኢኮኖሚን እውን ለማድረግ የተጠቀመችበት ታላቅ የድል ምዕራፍ ነው።
በመርሐ ግብሩ የተመዘገበውን ድል የዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ዕውቅና የሰጠው ሲሆን፤ በተለያዩ አጋጣሚዎችም ኢትዮጵያ ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ኢኮኖሚ ለመገንባት የምታደርገውን ጥረት አድንቋል።
የተባበሩት መንግሥታት የአየር ንብረት ጉባኤ (ኮፕ-32) በኢትዮጵያ እንዲዘጋጅ የተወሰነውም ለኢትዮጵያ ጥረት ዕውቅና በመስጠት ነው።
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 28፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር የግብርና ምርታማነትን ማሳደግን ጨምሮ ዘርፈ ብዙ ሀገራዊ ጠቀሜታዎችን እያበረከተ ነው፡፡
መርሐ ግብሩ የአካባቢ ጥበቃ ሚናውን በጥቂት ዓመታት ብቻ ከፍ አድርጓል፡፡ የአፈር መሸርሸርን በመከላከል እና የደን ሽፋንን በማሳደግ ረገድ ከፍተኛ ውጤት አሳይቷል።
ይህ ንቅናቄ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀሳብ አመንጪነት ከ2011 ዓ.ም ጀምሮ ሲተገበር ቆይቷል። በዚህም የዘንድሮውን ሳይጨምር ከ48 ቢሊየን በላይ ችግኞችን በመትከል ስኬት ተመዝግቦበታል።
የመላው ኢትዮጵያውያን ላብ ውጤት የሆነው አረንጓዴ ዐሻራ የአየር ንብረት ለውጥን እና የተፈጥሮ ሀብት መመናመንን ለመላቀቅ፣ ለምግብ ዋስትናና ለሥራ ዕድል ፈጠራ የተተለመ ትውልድ ተሻጋሪ እቅድ ነው።
የአየር ንብረት ለውጥ ተግዳሮትና የደን መመናመን የአፈር መሸርሸር እና የውሃ አካላት መድረቅ ፈተናዎችን አስከትሎ ነበር፡፡ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር በቁርጠኝነት መተግበሩ የደን መመናመንን በማስቀረት የአየር ንብረት ለውጥ ጫናን ለመቋቋም የሚያስችል አቅም ፈጥሯል።
በዚህም የአፈር መከላት ችግር ቀደም ሲል ከነበረው አንጻር በ50 በመቶ ያህል መቀነስ መቻሉ እና የውሃ አካላት በደለል የመሞላት ችግር መፈታቱ ዘርፈ ብዙ ጥቅም እየሰጠ ይገኛል።
ይህም የምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥ ባለፈ ፍራፍሬዎችን ጨምሮ የተለያዩ የግብርና ምርቶችን ወደ ውጭ የመላክ አቅሟን ለማሳደግ በቅታለች፡፡
የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር ህጻናትን፣ አዛውንቶችን፣ ወጣቶችን እና የመንግሥት ሰራተኞችን ጨምሮ መላውን ህዝብ አሳትፏል፡፡
መርሐ ግብሩ የተፈጥሮ ሀብትን ከመጠበቅ ባለፈ ሰፊ የስራ ዕድል ፈጥሯል።
የመላው ኢትዮጵያውያን የጋራ ላብ ውጤት የሆነው አረንጓዴ አሻራ ዛሬ ላይ የሚታይ ተጨባጭ የለምለም ተፈጥሮ መሠረት ብቻ ሳይሆን ለቀጣዩ ትውልድ ንጹህ አየር፣ ውሃ እና አፈርን የማስተላለፍ ዋስትና ነው።
ይህ ህዝባዊ ንቅናቄ ኢትዮጵያ ለአካባቢ ጥበቃ ያላትን ጽኑ ቁርጠኝነት ለዓለም ያስመሰከረችበት እና አረንጓዴ ኢኮኖሚን እውን ለማድረግ የተጠቀመችበት ታላቅ የድል ምዕራፍ ነው።
በመርሐ ግብሩ የተመዘገበውን ድል የዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ዕውቅና የሰጠው ሲሆን፤ በተለያዩ አጋጣሚዎችም ኢትዮጵያ ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ኢኮኖሚ ለመገንባት የምታደርገውን ጥረት አድንቋል።
የተባበሩት መንግሥታት የአየር ንብረት ጉባኤ (ኮፕ-32) በኢትዮጵያ እንዲዘጋጅ የተወሰነውም ለኢትዮጵያ ጥረት ዕውቅና በመስጠት ነው።
12 hours ago
ቀብር
#ethiopia | የብሔራዊ ሎተሪ አስተዳደር ዋና ሥራ አስኪያጅነትና በተለያዩ መስሪያ ቤቶች ከ40 ዓመታት በላይ በኃላፊነት ሲሠሩ የነበሩት ወይዘሮ መዓዛ ቅጣው አረፉ።
ወይዘሮ መዓዛ ቅጣው በ83 ዓመታቸው ያረፉት ሐምሌ 27 ቀን 2018 ዓ.ም. በአጋጠማቸው ድንገተኛ ሕመም ነው።
ወይዘሮ መዓዛ ቅጣው ሴቶች ከዩኒቨርሲቲ ለመመረቅና በከፍተኛ ኃላፊነት ተመድበው ለመሥራት ብርቅ በነበረበት ጊዜ በውጤት ያለፉ፣ በፋና ወጊነት በሚቆጠር አርአያነት፣ በከፍተኛ ተሳትፎ ሀገራቸውን ሲያገለግሉ ቆይተዋል።
በ1950ዎቹ መጨረሻ ከቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ በኢኮኖሚክስ የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን፣ ከዋሺንግተን ዲሲ አሜሪካን ዩኒቨርሲቲ ሁለተኛ ዲግሪያቸውን በማግኘት ለወጣት ሴቶች ምሳሌ ለመሆን የበቁ ነበሩ።
ወይዘሮ መዓዛ ቅጣው ከ40 ዓመታት በላይ በኃላፊነትና በሥራ መሪነት ባገለገሉባቸው የግልና የመንግሥት መስሪያ ቤቶች አዳዲስ የሥራ ዘዴዎችን በመቀየስና የተቀናጀ አሠራር በማስለመድ ስማቸው በመልካም ሲጠራ ቆይቷል።
በተለይም ለ19 ዓመታት በዋና ሥራ አስኪያጅነት የመሩትን የብሔራዊ ሎተሪ አስተዳደር ትርፋማ ለማድረግ፣ አሠራሩን ለማዘመንና ጠንካራ ተቋም እንዲሆን ያበረከቱት አስተዋጽኦ በጊዜው በነበሩትና ሰነድ በሚመረምሩት ዘንድ የታወቀ ነው።
እንደ ፈጣን ሎተሪ ዓይነቶቹ ከጊዜው ጋር የተጣጣሙ አሠራሮች በብሔራዊ ሎተሪ አስተዳደር እንዲለመዱና የተጠናከሩ እንዲሆኑ ያደረጉት ወይዘሮ መዓዛ ቅጣው ናቸው።
በኢትዮጵያ መድን ድርጅት፣ በኅብረት ኢንሹራንስ፣ በናይል ኢንሹራንስ፣ በብርሃን ኢንሹራንስ በመመሪያ ሥራ አስኪያጅነት እየተመደቡ ተቋሞቹ እንዲጠናከሩ ሙሉ ልምዳቸውንና ችሎታቸውን ማስተላለፋቸውን አብረዋቸው የሠሩት እየመሰከሩላቸው ነው።
ወይዘሮ መዓዛ ቅጣው ትኩረትና ጥንቃቄ ከሚጠይቀው የሥራ መደባቸው ጋር ደርበው እንደ ቤተሰብ መመሪያ ማኅበር ከአንዴም ሁለቴ፣ እንደ ቀይ መስቀል ማኅበር፣ እንደ ኢየሩሳሌም የሕፃናት ማሳደጊያ ድርጅትና በመሣሰሉት ተቋማት ለረጅም ዓመታት በቦርድ ሊቀ መንበርነትና አባልነት፣ በሥራ አስፈጻሚነትም ጭምር ሲሠሩ ቆይተዋል።
ዘለግ ላለውና ውጤታማ ለሆነ ሥራቸው የተለያዩ ሽልማቶችን አግኝተዋል።
እስከ ሕልፈታቸው ድረስ ከሥራ ሳይለዩ በጥናትና በምርምር ሥር ቆይተዋል።
የሁለት ልጆች የሆኑት ወይዘሮ መዓዛ ቅጣው የቀብር ሥነ ሥርዓት ኮተቤ በሚገኘው በመካነ ቅዱሳን ሐና ወኢያቄም ቤተ ክርስቲያን ሐሙስ ሐምሌ 30 ቀን 2018 ዓ.ም. ከቀኑ በ6:00 ሰዓት እንደሚፈጸም ቤተሰቦቻቸው ነግረውናል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#ethiopia | የብሔራዊ ሎተሪ አስተዳደር ዋና ሥራ አስኪያጅነትና በተለያዩ መስሪያ ቤቶች ከ40 ዓመታት በላይ በኃላፊነት ሲሠሩ የነበሩት ወይዘሮ መዓዛ ቅጣው አረፉ።
ወይዘሮ መዓዛ ቅጣው በ83 ዓመታቸው ያረፉት ሐምሌ 27 ቀን 2018 ዓ.ም. በአጋጠማቸው ድንገተኛ ሕመም ነው።
ወይዘሮ መዓዛ ቅጣው ሴቶች ከዩኒቨርሲቲ ለመመረቅና በከፍተኛ ኃላፊነት ተመድበው ለመሥራት ብርቅ በነበረበት ጊዜ በውጤት ያለፉ፣ በፋና ወጊነት በሚቆጠር አርአያነት፣ በከፍተኛ ተሳትፎ ሀገራቸውን ሲያገለግሉ ቆይተዋል።
በ1950ዎቹ መጨረሻ ከቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ በኢኮኖሚክስ የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን፣ ከዋሺንግተን ዲሲ አሜሪካን ዩኒቨርሲቲ ሁለተኛ ዲግሪያቸውን በማግኘት ለወጣት ሴቶች ምሳሌ ለመሆን የበቁ ነበሩ።
ወይዘሮ መዓዛ ቅጣው ከ40 ዓመታት በላይ በኃላፊነትና በሥራ መሪነት ባገለገሉባቸው የግልና የመንግሥት መስሪያ ቤቶች አዳዲስ የሥራ ዘዴዎችን በመቀየስና የተቀናጀ አሠራር በማስለመድ ስማቸው በመልካም ሲጠራ ቆይቷል።
በተለይም ለ19 ዓመታት በዋና ሥራ አስኪያጅነት የመሩትን የብሔራዊ ሎተሪ አስተዳደር ትርፋማ ለማድረግ፣ አሠራሩን ለማዘመንና ጠንካራ ተቋም እንዲሆን ያበረከቱት አስተዋጽኦ በጊዜው በነበሩትና ሰነድ በሚመረምሩት ዘንድ የታወቀ ነው።
እንደ ፈጣን ሎተሪ ዓይነቶቹ ከጊዜው ጋር የተጣጣሙ አሠራሮች በብሔራዊ ሎተሪ አስተዳደር እንዲለመዱና የተጠናከሩ እንዲሆኑ ያደረጉት ወይዘሮ መዓዛ ቅጣው ናቸው።
በኢትዮጵያ መድን ድርጅት፣ በኅብረት ኢንሹራንስ፣ በናይል ኢንሹራንስ፣ በብርሃን ኢንሹራንስ በመመሪያ ሥራ አስኪያጅነት እየተመደቡ ተቋሞቹ እንዲጠናከሩ ሙሉ ልምዳቸውንና ችሎታቸውን ማስተላለፋቸውን አብረዋቸው የሠሩት እየመሰከሩላቸው ነው።
ወይዘሮ መዓዛ ቅጣው ትኩረትና ጥንቃቄ ከሚጠይቀው የሥራ መደባቸው ጋር ደርበው እንደ ቤተሰብ መመሪያ ማኅበር ከአንዴም ሁለቴ፣ እንደ ቀይ መስቀል ማኅበር፣ እንደ ኢየሩሳሌም የሕፃናት ማሳደጊያ ድርጅትና በመሣሰሉት ተቋማት ለረጅም ዓመታት በቦርድ ሊቀ መንበርነትና አባልነት፣ በሥራ አስፈጻሚነትም ጭምር ሲሠሩ ቆይተዋል።
ዘለግ ላለውና ውጤታማ ለሆነ ሥራቸው የተለያዩ ሽልማቶችን አግኝተዋል።
እስከ ሕልፈታቸው ድረስ ከሥራ ሳይለዩ በጥናትና በምርምር ሥር ቆይተዋል።
የሁለት ልጆች የሆኑት ወይዘሮ መዓዛ ቅጣው የቀብር ሥነ ሥርዓት ኮተቤ በሚገኘው በመካነ ቅዱሳን ሐና ወኢያቄም ቤተ ክርስቲያን ሐሙስ ሐምሌ 30 ቀን 2018 ዓ.ም. ከቀኑ በ6:00 ሰዓት እንደሚፈጸም ቤተሰቦቻቸው ነግረውናል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
13 hours ago
የፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን ለመቄዶንያ ከ4.6 ሚሊዮን ብር በላይ ድጋፍ አበረከተ
#ethiopia | አዲስ አበባ | ኢትዮጵያ – የፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን የመስሪያ ቤቱን ማኔጅመንት፣ ሰራተኞች እና ታራሚዎች በማስተባበር ለመቄዶንያ አረጋውያንና ህጻናት መረዳጃ ማህበር ከ4.6 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት የገንዘብና የአይነት ድጋፍ አበርክቷል።
ኮሚሽኑ ቀደም ሲል በገባው ቃል መሰረት በየዓመቱ ሐምሌ 28 መቄዶንያን የመጎብኘት ልማዱን በመቀጠል፣ በዚህ ዓመትም 547 ሺህ 65 ብር ጥሬ ገንዘብ እና ከ4.1 ሚሊዮን ብር በላይ የሚያወጡ የተለያዩ ቁሳቁሶችን ለማህበሩ አስረክቧል።
የፌዴራል ማረሚያ ቤት ዋና ኮሚሽነር የኑስ ሙሉ፣ መቄዶንያ ለሚያከናውነው ሰብዓዊ አገልግሎት በኮሚሽኑ ስም ያላቸውን አክብሮትና ምስጋና ገልጸዋል።
በጉብኝቱ ወቅት የኮሚሽኑ የህክምና ልዑካን ቡድን ከ770 ሺህ ብር በላይ የሚገመቱ የህክምና ቁሳቁሶችን በማበርከት ብቻ ሳይሆን፣ ለማህበሩ ተገልጋዮች የህክምና አገልግሎትም ሰጥቷል።
በተጨማሪም በኮሚሽኑ ስር የሚገኙ ታራሚዎች በእጃቸው ያመረቷቸውን የተለያዩ ቁሳቁሶች በስጦታ በማበርከት ከመልካም ምኞት መልዕክታቸው ጋር ለማህበሩ አስረክበዋል።
የመቄዶንያ መስራችና ዋና ሥራ አስኪያጅ ክቡር ዶ/ር ቢንያም በለጠ ለተደረገው ድጋፍ ምስጋና ያቀረቡ ሲሆን፣ የማህበሩ ተገልጋይ አረጋውያንም በተደረገላቸው ጉብኝትና ድጋፍ ያላቸውን ደስታ ገልጸዋል።
ጌጡ ተመስገን
#ethiopia #federalprisoncommission #macedonia #charitysupport #givingback #humanitarianassociation #getutemesgen #ጌጡተመስገን
#ethiopia | አዲስ አበባ | ኢትዮጵያ – የፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን የመስሪያ ቤቱን ማኔጅመንት፣ ሰራተኞች እና ታራሚዎች በማስተባበር ለመቄዶንያ አረጋውያንና ህጻናት መረዳጃ ማህበር ከ4.6 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት የገንዘብና የአይነት ድጋፍ አበርክቷል።
ኮሚሽኑ ቀደም ሲል በገባው ቃል መሰረት በየዓመቱ ሐምሌ 28 መቄዶንያን የመጎብኘት ልማዱን በመቀጠል፣ በዚህ ዓመትም 547 ሺህ 65 ብር ጥሬ ገንዘብ እና ከ4.1 ሚሊዮን ብር በላይ የሚያወጡ የተለያዩ ቁሳቁሶችን ለማህበሩ አስረክቧል።
የፌዴራል ማረሚያ ቤት ዋና ኮሚሽነር የኑስ ሙሉ፣ መቄዶንያ ለሚያከናውነው ሰብዓዊ አገልግሎት በኮሚሽኑ ስም ያላቸውን አክብሮትና ምስጋና ገልጸዋል።
በጉብኝቱ ወቅት የኮሚሽኑ የህክምና ልዑካን ቡድን ከ770 ሺህ ብር በላይ የሚገመቱ የህክምና ቁሳቁሶችን በማበርከት ብቻ ሳይሆን፣ ለማህበሩ ተገልጋዮች የህክምና አገልግሎትም ሰጥቷል።
በተጨማሪም በኮሚሽኑ ስር የሚገኙ ታራሚዎች በእጃቸው ያመረቷቸውን የተለያዩ ቁሳቁሶች በስጦታ በማበርከት ከመልካም ምኞት መልዕክታቸው ጋር ለማህበሩ አስረክበዋል።
የመቄዶንያ መስራችና ዋና ሥራ አስኪያጅ ክቡር ዶ/ር ቢንያም በለጠ ለተደረገው ድጋፍ ምስጋና ያቀረቡ ሲሆን፣ የማህበሩ ተገልጋይ አረጋውያንም በተደረገላቸው ጉብኝትና ድጋፍ ያላቸውን ደስታ ገልጸዋል።
ጌጡ ተመስገን
#ethiopia #federalprisoncommission #macedonia #charitysupport #givingback #humanitarianassociation #getutemesgen #ጌጡተመስገን
1 day ago
#tecno_spark_50
አዲሱ የቴክኖ ስፓርክ 50 ስልክ ጥርት ያለ ስክሪኑ የተለያዩ ስራዎችን ለመስራት፣ ማህበራዊ ሚዲያ ለመጠቀም ወይንም ፎቶ እና ቪዲዮችን ኤዲት ለማድረግ 120 Hz ፈጣን እና 6 ነጥብ 78 ኢንች ስክሪኑ ፍጥነት እና ጥራትን አብሮ ይሰጦታል፡፡ ይሄ ዘርፈ ብዙ ስልክ ያለ ምንም ጥርጥር ይገባዎታል፡፡
#spark50 #spark50series #tecnoai #tecnoet
tecno_et
አዲሱ የቴክኖ ስፓርክ 50 ስልክ ጥርት ያለ ስክሪኑ የተለያዩ ስራዎችን ለመስራት፣ ማህበራዊ ሚዲያ ለመጠቀም ወይንም ፎቶ እና ቪዲዮችን ኤዲት ለማድረግ 120 Hz ፈጣን እና 6 ነጥብ 78 ኢንች ስክሪኑ ፍጥነት እና ጥራትን አብሮ ይሰጦታል፡፡ ይሄ ዘርፈ ብዙ ስልክ ያለ ምንም ጥርጥር ይገባዎታል፡፡
#spark50 #spark50series #tecnoai #tecnoet
tecno_et
1 day ago
"ደቦ" የጥንቱ የኢትዮጵያውያን ትብብር ለዘመናዊው የአካባቢ ጥበቃ
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 27፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ኢትዮጵያውያን በዚህ ክረምት የደቦ (ጅጌ) ሥራ አለባቸው፡፡ ሀገራቸው ደግሳ ልጆቿን ለብርቱ ሥራ ጋብዛለች - ለአረንጓዴ ዐሻራ፡፡
በተለያዩ የኢትዮጵያ ማሕበረሰቦች ባህል፣ የአንድነት፣ የደግነት፣ የትብብር እና የጋራ ጥንካሬ ትልቁ መገለጫ «ደቦ» ወይም በአንዳንድ አካባቢዎች «ጅጌ» ተብሎ የሚጠራው ሥርዓት ነው።
ይህ ከትውልድ ወደ ትውልድ የተሻገረ የጋራ የሥራ ባህል፣ ግለሰቦች ብቻቸውን ሊወጡት የማይችሉትን ከባድ የግብርና፣ የቤት ግንባታ እና የማኅበራዊ ሕይወት ፈተናዎች በአንድነት ለማሸነፍ የሚያስችል ጥንታዊ መፍትሔ ነው።
ዛሬ ላይ ይህ ታላቅ ማኅበራዊ እሴት አዲስ መልክና ብሔራዊ ግብ አንግቦ በኢትዮጵያ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር ላይ በደመቀ ሁኔታ እየተተገበረ ይገኛል።
ይህን ጥንታዊ የማሕበረሰብ ዕውቀት ዛሬ ሐምሌ 27 ቀን 2018 ዓ.ም. ከ805 ነጥብ 3 ሚሊየን በላይ ችግኞችን በመትከል በወሳኝ ብሔራዊ ጉዳይ ላይ ተግባራዊ ተደርጓል፡፡
ደቦ በባህሪው ለአንድ አምራች ወይም ባለሥራ ሳምንታት ሊፈጅ የሚችልን የአዝመራ ስብሰባ ወይም የአፈር ጥበቃ ሥራ በጥቂት ሰዓታት ውስጥ በማጠናቀቅ ጊዜንና ጉልበትን ለመቆጠብ ያስችላል፡፡
ኢትዮጵያም በዚህ የክረምቱ ወቅት ልትተክል ያሰበችውን 8 ቢሊየን ችግኝ እቅድ ማሳካት የሚያስችላትን ከፍ ያለ ሥራ ከውናለች፡፡
ክረምቱ ከገባበት ጊዜ እንስቶ እስካሁን ድረስ 6 ነጥብ 5 ቢሊየን ችግኞች የተተከሉ ሲሆን፣ ዛሬ በሐምሌ 27 ቀን 2018 ዓ.ም ብቻ ከ805 ነጥብ 3 ሚሊየን በላይ ችግኞችን በመትከል ከእቅድ በላይ ማሳካት ተችሏል፡፡
በሰዎች መካከል መተባበርን፣ መከባበርንና ማኅበራዊ ትስስርን የሚያጠናክረው የደቦ ሥርዓት አሁን በአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር ላይም ተግባራዊ ተደርጓል፡፡ በሚሊየን የሚቆጠሩ ዜጎች ለሀገራቸው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር በአንድ እንዲቆሙ አድርጓል፣ አስተባብሯልም፡፡
የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር በየዓመቱ በተሳካ ሁኔታ እንዲቀጥል ያደረገው ዋናው ሞተርም ይህ የቆየው የደቦ (ጂጌ) ባህል ነው።
በሚሊየን የሚቆጠሩ የተለያዩ የችግኝ ዝርያዎችን በአጭር ጊዜ ውስጥ ለመትከል የመንግሥት መዋቅር ብቻውን በቂ ባለመሆኑ የጂጌ መንፈስ እንደ ዋና መፍትሔ ሆኖ አገልግሏል።
ልክ ለአዝመራ መሰብሰብ እንደምንሰባሰበው ሁሉ፣ ዛሬም የመንግሥት ሠራተኛው፣ አርሶ አደሩ፣ ተማሪዎቸ፣ የኃይማኖት መሪዎች፣ ሴቶች ፣ወንዶች ፣ህጻናቱ ሳይቀሩ በአንድነት ብርዱ እና ክረምቱ ቅዝቃዜ ሳይበግራቸው ወደ ችግኝ መትከያ ቦታዎች በመትመም ዐሻራቸውን አኑረዋል፡፡
ደቦ «የወንድሜ ሥራ የኔም ሥራ ነው» የሚል እሳቤ አለው። የአረንጓዴ አሻራ ንቅናቄም «የሀገር ስራ የሁሉም ትውልድ ሥራ ነው፣ ሀገር የሁሉም በመሆኗ አካባቢን የመጠበቅ ኃላፊነትም የጋራ ነው» የሚል ተመሳሳይ መርህን ይከተላል።
በችግኝ ተከላው ወቅት በአባቶች እናቶችና ወጣቶች ዘንድ የሚታየው የትብብር ትዕይንት ዕድሜ ጠገቡ የሀገር ቤት የደቦ ሥርዓት በትልልቅ ብሔራዊ መድረኮች ለትውልድ ግንባታ እየዋለ ለመሆኑ ጠቋሚ ነው፡፡
የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር በአንድ በኩል የአየር ንብረት ለውጥን ለመከላከልና የሀገሪቱን የደን ሽፋን ለማሳደግ የሚደረገውን ጥረት ሲያግዝ በሌላ በኩል ደግሞ በቴክኖሎጂና በዘመናዊነት ምክንያት እየጠፋ የመጣውን የትብብር ባህል አዲሱ ትውልድ በተግባር እንዲማረውና እንዲረከበው በር ከፍቷል።
ባጭሩ የአረንጓዴ ዐሻራ ስኬት የኢትዮጵያውያን ጥንታዊ የደቦ ባህል ዛሬም ሕያው መሆኑን እና ለዘመናዊ ዓለም አቀፋዊ ችግሮች እንደ አካባቢ መራቆት ያሉ ፈተናዎች ሀገር በቀል መፍትሔ መሆን እንደሚችል ያሳየበት ታላቅ ማረጋገጫ ነው።
ኢትዮጵያም ባለፉት 7 ዓመታት ልጆቿን አሰባስባ ከ48 ቢሊየን በላይ ችግኞችን ተክላለች፡፡ በዛሬው ዕለት ደግሞ በአንድ ጀምበር ልጆቿን ደቦ ጠርታ ከ805 ነጥብ 3 ሚሊየን በላይ ችግኞችን መትከል ችላለች፡፡
በእመቤት ሲሳይ
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 27፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ኢትዮጵያውያን በዚህ ክረምት የደቦ (ጅጌ) ሥራ አለባቸው፡፡ ሀገራቸው ደግሳ ልጆቿን ለብርቱ ሥራ ጋብዛለች - ለአረንጓዴ ዐሻራ፡፡
በተለያዩ የኢትዮጵያ ማሕበረሰቦች ባህል፣ የአንድነት፣ የደግነት፣ የትብብር እና የጋራ ጥንካሬ ትልቁ መገለጫ «ደቦ» ወይም በአንዳንድ አካባቢዎች «ጅጌ» ተብሎ የሚጠራው ሥርዓት ነው።
ይህ ከትውልድ ወደ ትውልድ የተሻገረ የጋራ የሥራ ባህል፣ ግለሰቦች ብቻቸውን ሊወጡት የማይችሉትን ከባድ የግብርና፣ የቤት ግንባታ እና የማኅበራዊ ሕይወት ፈተናዎች በአንድነት ለማሸነፍ የሚያስችል ጥንታዊ መፍትሔ ነው።
ዛሬ ላይ ይህ ታላቅ ማኅበራዊ እሴት አዲስ መልክና ብሔራዊ ግብ አንግቦ በኢትዮጵያ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር ላይ በደመቀ ሁኔታ እየተተገበረ ይገኛል።
ይህን ጥንታዊ የማሕበረሰብ ዕውቀት ዛሬ ሐምሌ 27 ቀን 2018 ዓ.ም. ከ805 ነጥብ 3 ሚሊየን በላይ ችግኞችን በመትከል በወሳኝ ብሔራዊ ጉዳይ ላይ ተግባራዊ ተደርጓል፡፡
ደቦ በባህሪው ለአንድ አምራች ወይም ባለሥራ ሳምንታት ሊፈጅ የሚችልን የአዝመራ ስብሰባ ወይም የአፈር ጥበቃ ሥራ በጥቂት ሰዓታት ውስጥ በማጠናቀቅ ጊዜንና ጉልበትን ለመቆጠብ ያስችላል፡፡
ኢትዮጵያም በዚህ የክረምቱ ወቅት ልትተክል ያሰበችውን 8 ቢሊየን ችግኝ እቅድ ማሳካት የሚያስችላትን ከፍ ያለ ሥራ ከውናለች፡፡
ክረምቱ ከገባበት ጊዜ እንስቶ እስካሁን ድረስ 6 ነጥብ 5 ቢሊየን ችግኞች የተተከሉ ሲሆን፣ ዛሬ በሐምሌ 27 ቀን 2018 ዓ.ም ብቻ ከ805 ነጥብ 3 ሚሊየን በላይ ችግኞችን በመትከል ከእቅድ በላይ ማሳካት ተችሏል፡፡
በሰዎች መካከል መተባበርን፣ መከባበርንና ማኅበራዊ ትስስርን የሚያጠናክረው የደቦ ሥርዓት አሁን በአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር ላይም ተግባራዊ ተደርጓል፡፡ በሚሊየን የሚቆጠሩ ዜጎች ለሀገራቸው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር በአንድ እንዲቆሙ አድርጓል፣ አስተባብሯልም፡፡
የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር በየዓመቱ በተሳካ ሁኔታ እንዲቀጥል ያደረገው ዋናው ሞተርም ይህ የቆየው የደቦ (ጂጌ) ባህል ነው።
በሚሊየን የሚቆጠሩ የተለያዩ የችግኝ ዝርያዎችን በአጭር ጊዜ ውስጥ ለመትከል የመንግሥት መዋቅር ብቻውን በቂ ባለመሆኑ የጂጌ መንፈስ እንደ ዋና መፍትሔ ሆኖ አገልግሏል።
ልክ ለአዝመራ መሰብሰብ እንደምንሰባሰበው ሁሉ፣ ዛሬም የመንግሥት ሠራተኛው፣ አርሶ አደሩ፣ ተማሪዎቸ፣ የኃይማኖት መሪዎች፣ ሴቶች ፣ወንዶች ፣ህጻናቱ ሳይቀሩ በአንድነት ብርዱ እና ክረምቱ ቅዝቃዜ ሳይበግራቸው ወደ ችግኝ መትከያ ቦታዎች በመትመም ዐሻራቸውን አኑረዋል፡፡
ደቦ «የወንድሜ ሥራ የኔም ሥራ ነው» የሚል እሳቤ አለው። የአረንጓዴ አሻራ ንቅናቄም «የሀገር ስራ የሁሉም ትውልድ ሥራ ነው፣ ሀገር የሁሉም በመሆኗ አካባቢን የመጠበቅ ኃላፊነትም የጋራ ነው» የሚል ተመሳሳይ መርህን ይከተላል።
በችግኝ ተከላው ወቅት በአባቶች እናቶችና ወጣቶች ዘንድ የሚታየው የትብብር ትዕይንት ዕድሜ ጠገቡ የሀገር ቤት የደቦ ሥርዓት በትልልቅ ብሔራዊ መድረኮች ለትውልድ ግንባታ እየዋለ ለመሆኑ ጠቋሚ ነው፡፡
የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር በአንድ በኩል የአየር ንብረት ለውጥን ለመከላከልና የሀገሪቱን የደን ሽፋን ለማሳደግ የሚደረገውን ጥረት ሲያግዝ በሌላ በኩል ደግሞ በቴክኖሎጂና በዘመናዊነት ምክንያት እየጠፋ የመጣውን የትብብር ባህል አዲሱ ትውልድ በተግባር እንዲማረውና እንዲረከበው በር ከፍቷል።
ባጭሩ የአረንጓዴ ዐሻራ ስኬት የኢትዮጵያውያን ጥንታዊ የደቦ ባህል ዛሬም ሕያው መሆኑን እና ለዘመናዊ ዓለም አቀፋዊ ችግሮች እንደ አካባቢ መራቆት ያሉ ፈተናዎች ሀገር በቀል መፍትሔ መሆን እንደሚችል ያሳየበት ታላቅ ማረጋገጫ ነው።
ኢትዮጵያም ባለፉት 7 ዓመታት ልጆቿን አሰባስባ ከ48 ቢሊየን በላይ ችግኞችን ተክላለች፡፡ በዛሬው ዕለት ደግሞ በአንድ ጀምበር ልጆቿን ደቦ ጠርታ ከ805 ነጥብ 3 ሚሊየን በላይ ችግኞችን መትከል ችላለች፡፡
በእመቤት ሲሳይ
2 days ago
ፋሻ ላውንጅ ሀዋሳ
– የመዝናኛዎ አዲሱ መዳረሻ!
ሀዋሳን በልዩ መንገድ ለመዝናናት ይፈልጋሉ?
ፋሻ ላውንጅ ሀዋሳ ለከተማው ነዋሪዎች ብቻ ሳይሆን ከየትኛውም ስፍራ ለሚመጡ እንግዶች የተለየ የመዝናኛ ልምድ ያቀርባል።
🌴 ነፋሻማና ዘመናዊ አካባቢ
🎧 በምርጥ ዲጄዎች የተሞላ አስደሳች ሙዚቃ
🍽️ ጣፋጭ ምግቦችና የተለያዩ መጠጦች
🤝 ፈጣንና ሙያዊ አገልግሎት
✨ ለወዳጅ ስብሰባ፣ ለቤተሰብ መዝናኛ እና ለልዩ ዝግጅቶች ተስማሚ
ደማቅ ቀንም ሆነ አስደሳች ምሽት በሀዋሳ ማሳለፍ ከፈለጉ፣ ፋሻ ላውንጅ የመጀመሪያ ምርጫዎ ነው።
አድራሻ: ሀዋሳ 05፣ ከጉዱማሌ ፊት ለፊት
ስልክ +251-916-860330
ፋሻ ላውንጅ ሀዋሳ
ይምጡ... ይዝናኑ... የማይረሳ ትዝታ ይዘው ይመለሱ!
– የመዝናኛዎ አዲሱ መዳረሻ!
ሀዋሳን በልዩ መንገድ ለመዝናናት ይፈልጋሉ?
ፋሻ ላውንጅ ሀዋሳ ለከተማው ነዋሪዎች ብቻ ሳይሆን ከየትኛውም ስፍራ ለሚመጡ እንግዶች የተለየ የመዝናኛ ልምድ ያቀርባል።
🌴 ነፋሻማና ዘመናዊ አካባቢ
🎧 በምርጥ ዲጄዎች የተሞላ አስደሳች ሙዚቃ
🍽️ ጣፋጭ ምግቦችና የተለያዩ መጠጦች
🤝 ፈጣንና ሙያዊ አገልግሎት
✨ ለወዳጅ ስብሰባ፣ ለቤተሰብ መዝናኛ እና ለልዩ ዝግጅቶች ተስማሚ
ደማቅ ቀንም ሆነ አስደሳች ምሽት በሀዋሳ ማሳለፍ ከፈለጉ፣ ፋሻ ላውንጅ የመጀመሪያ ምርጫዎ ነው።
አድራሻ: ሀዋሳ 05፣ ከጉዱማሌ ፊት ለፊት
ስልክ +251-916-860330
ፋሻ ላውንጅ ሀዋሳ
ይምጡ... ይዝናኑ... የማይረሳ ትዝታ ይዘው ይመለሱ!
2 days ago
በኦቶና ሆስፒታል የላብራቶሪ መሳሪያዎችን ሊሰርቅ የነበረ የጥበቃ ሰራተኛ እጅ ከፍንጂ ተያዘ
በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ኮምፕሬሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል (ኦቶና) ሦስት ወሳኝ የላብራቶሪ ማይክሮስኮፖችን አውጥቶ ለመሰወር ሲሞክር የነበረ የጥበቃ ሰራተኛ በተረኛ ጥበቃዎች ብርቱ ክትትልና ተጋድሎ እጅ ከፍንጂ መያዙ ተገለጸ።
በትላትናው እለተ የተፈጸመው ይህ ድርጊት ተራ የሕክምና ዕቃ ስርቆት ሳይሆን፣ የሺዎችን ሕይወት እና የሆስፒታሉን ዕለታዊ የሕክምና አገልግሎት ቀጥተኛ አደጋ ላይ የጣለ ከባድ ወንጀል መሆኑን ባለሙያዎች ይናገራሉ።
ተጠርጣሪው ግለሰብ የሕክምና መገልገያዎቹን ደብቆ ከሆስፒታሉ ግቢ ሊያወጣ ሲል በተረኛ ባልደረቦቹ ንቁ ክትትል በቁጥጥር ስር ውሏል። ድርጊቱ በግለሰቡ ብቻ የተፈጸመ ሳይሆን በጀርባ ያሉ አመቻቾችና አቀናባሪዎች እንዳሉበት በመጠረጠሩ፣ ወንጀሉን ያስተባበሩ አካላት በሙሉ ተለይተው ተገቢው የሕግ ትርጉም እንዲሰጣቸውና አስተማሪ ቅጣት እንዲያገኙ ጉዳዩ በትኩረት እየተከታተለ ይገኛል።
በአንድ አጠቃላይ ሆስፒታል ውስጥ ማይክሮስኮፕ ማለት የተደበቁ በሽታዎችን አውጥቶ በማሳየት የሕሙማንን ሕይወት የሚያስጥል ዋና መመርመሪያ መሳሪያ ነው።
እነዚህን መገልገያዎች ማጣት በሕሙማን ላይ የሚከተሉትን ከባድ የጤና አደጋዎች ያስከትላል፦
እንደ ወባ፣ ቲቢ እና የተለያዩ ከባድ የባክቴሪያ ኢንፌክሽኖችን በፍጥነት በመመርመር አስቸኳይ የሕክምና ውሳኔ ለመስጠት ያገለግላሉ።
የደም ማነስን (Anemia) እና የደም ካንሰርን (Leukemia) በጥንቃቄ ለይቶ ለማወቅ ወሳኝ መገልገያዎች ናቸው።
እነዚህ መሳሪያዎች ከአገልግሎት ውጭ ሲሆኑ የላብራቶሪ ውጤቶች ይዘገያሉ፤ ይህም በተለይ በፅኑ ሕሙማን፣ በሕፃናትና ነፍሰ ጡራት ሕይወት ላይ የቀጥታ አደጋ ይደቅናል።
የሕዝብና የመንግሥት ሀብት የሆኑትን የሕክምና መገልገያዎች ከስርቆትና ከእጅ አዙር ሴራ መጠበቅ የሁላችንም ኃላፊነት ነው።
በሆስፒታሉ ግቢ ውስጥ የታየው የተረኛ ጥበቃዎች ንቅናቄ የሚደነቅ ሲሆን፣ የወንጀሉ ተሳታፊዎች በሙሉ ለሕግ እንዲቀርቡ የጀመረው ክትትል ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል።
Via ጉርሻ page
በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ኮምፕሬሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል (ኦቶና) ሦስት ወሳኝ የላብራቶሪ ማይክሮስኮፖችን አውጥቶ ለመሰወር ሲሞክር የነበረ የጥበቃ ሰራተኛ በተረኛ ጥበቃዎች ብርቱ ክትትልና ተጋድሎ እጅ ከፍንጂ መያዙ ተገለጸ።
በትላትናው እለተ የተፈጸመው ይህ ድርጊት ተራ የሕክምና ዕቃ ስርቆት ሳይሆን፣ የሺዎችን ሕይወት እና የሆስፒታሉን ዕለታዊ የሕክምና አገልግሎት ቀጥተኛ አደጋ ላይ የጣለ ከባድ ወንጀል መሆኑን ባለሙያዎች ይናገራሉ።
ተጠርጣሪው ግለሰብ የሕክምና መገልገያዎቹን ደብቆ ከሆስፒታሉ ግቢ ሊያወጣ ሲል በተረኛ ባልደረቦቹ ንቁ ክትትል በቁጥጥር ስር ውሏል። ድርጊቱ በግለሰቡ ብቻ የተፈጸመ ሳይሆን በጀርባ ያሉ አመቻቾችና አቀናባሪዎች እንዳሉበት በመጠረጠሩ፣ ወንጀሉን ያስተባበሩ አካላት በሙሉ ተለይተው ተገቢው የሕግ ትርጉም እንዲሰጣቸውና አስተማሪ ቅጣት እንዲያገኙ ጉዳዩ በትኩረት እየተከታተለ ይገኛል።
በአንድ አጠቃላይ ሆስፒታል ውስጥ ማይክሮስኮፕ ማለት የተደበቁ በሽታዎችን አውጥቶ በማሳየት የሕሙማንን ሕይወት የሚያስጥል ዋና መመርመሪያ መሳሪያ ነው።
እነዚህን መገልገያዎች ማጣት በሕሙማን ላይ የሚከተሉትን ከባድ የጤና አደጋዎች ያስከትላል፦
እንደ ወባ፣ ቲቢ እና የተለያዩ ከባድ የባክቴሪያ ኢንፌክሽኖችን በፍጥነት በመመርመር አስቸኳይ የሕክምና ውሳኔ ለመስጠት ያገለግላሉ።
የደም ማነስን (Anemia) እና የደም ካንሰርን (Leukemia) በጥንቃቄ ለይቶ ለማወቅ ወሳኝ መገልገያዎች ናቸው።
እነዚህ መሳሪያዎች ከአገልግሎት ውጭ ሲሆኑ የላብራቶሪ ውጤቶች ይዘገያሉ፤ ይህም በተለይ በፅኑ ሕሙማን፣ በሕፃናትና ነፍሰ ጡራት ሕይወት ላይ የቀጥታ አደጋ ይደቅናል።
የሕዝብና የመንግሥት ሀብት የሆኑትን የሕክምና መገልገያዎች ከስርቆትና ከእጅ አዙር ሴራ መጠበቅ የሁላችንም ኃላፊነት ነው።
በሆስፒታሉ ግቢ ውስጥ የታየው የተረኛ ጥበቃዎች ንቅናቄ የሚደነቅ ሲሆን፣ የወንጀሉ ተሳታፊዎች በሙሉ ለሕግ እንዲቀርቡ የጀመረው ክትትል ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል።
Via ጉርሻ page
Sponsored by
Surafel
3 days ago
በጅማ ዞን ለሚካሄደው የአንድ ጀምበር ችግኝ ተከላ የተለያዩ እንግዶች ጅማ ገቡ!
በኦሮሚያ ክልል ጅማ ዞን ሰቃ ወረዳ በቡዬ ቀጨማ ቀበሌ ነገ ሐምሌ 27 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 12፡00 ሰዓት ጀምሮ የሚካሄደውና ለመላው ኢትዮጵያውያን ጥሪ የቀረበበት የአንድ ጀምበር የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር ዝግጅት መጠጠናቀቁ ተገለጸ። በአገር አቀፍ ደረጃ በአንድ ጀምበር ከ800 ሚሊዮን በላይ ችግኞችን ለመትከል በተያዘው ግብ መሠረት የሚከናወነው ይህ መርሃ-ግብር፤ አረንጓዴ አሻራን በማሳረፍ ረገድ የትውልድ ሀላፊነትን ለመወጣት ያለመ እንደሆነ ተነግሯል።
ይህ ሀገር አቀፍ አቅጣጫን መሠረት ያደረገ ታላቅ መርሃ-ግብር በግሪን ዌቭ አሊያንስ ሀገር በቀል ግብረ-ሰናይ ድርጅት፣ ከኢፌድሪ ግብርና ሚኒስቴር እና በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አዘጋጅነት የቀረበ ሲሆን፤ የኢትዮጵያ አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን እና የኦሮሚያ ግብርና ቢሮ አስፈላጊውን ቴክኒካል ድጋፍ በማድረግ ተሳትፏል።።
ለዝግጅቱ ስኬት በጅማ ከተማ የደረሱ ታዋቂ ግለሰቦች፣ አርቲስቶች፣ ጋዜጠኞች፣ ቲክቶክሮች እና የጥሪው ተጋባዦች በዞኑ እና በከተማ አስተዳደሩ፣ በአባ ገዳዎች፣ በሀደ ሲንቄዎች እንዲሁም በሀገር ሽማግሌዎች አቀባበል ተደርጎላቸዋል። ነገ በሚካሄደው በዚህ ታሪካዊ ኹነት ህብረተሰቡ በነቃ ሁኔታ እንዲሳተፍ አዘጋጆቹ ጥሪ አቅርበዋል።
በኦሮሚያ ክልል ጅማ ዞን ሰቃ ወረዳ በቡዬ ቀጨማ ቀበሌ ነገ ሐምሌ 27 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 12፡00 ሰዓት ጀምሮ የሚካሄደውና ለመላው ኢትዮጵያውያን ጥሪ የቀረበበት የአንድ ጀምበር የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር ዝግጅት መጠጠናቀቁ ተገለጸ። በአገር አቀፍ ደረጃ በአንድ ጀምበር ከ800 ሚሊዮን በላይ ችግኞችን ለመትከል በተያዘው ግብ መሠረት የሚከናወነው ይህ መርሃ-ግብር፤ አረንጓዴ አሻራን በማሳረፍ ረገድ የትውልድ ሀላፊነትን ለመወጣት ያለመ እንደሆነ ተነግሯል።
ይህ ሀገር አቀፍ አቅጣጫን መሠረት ያደረገ ታላቅ መርሃ-ግብር በግሪን ዌቭ አሊያንስ ሀገር በቀል ግብረ-ሰናይ ድርጅት፣ ከኢፌድሪ ግብርና ሚኒስቴር እና በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አዘጋጅነት የቀረበ ሲሆን፤ የኢትዮጵያ አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን እና የኦሮሚያ ግብርና ቢሮ አስፈላጊውን ቴክኒካል ድጋፍ በማድረግ ተሳትፏል።።
ለዝግጅቱ ስኬት በጅማ ከተማ የደረሱ ታዋቂ ግለሰቦች፣ አርቲስቶች፣ ጋዜጠኞች፣ ቲክቶክሮች እና የጥሪው ተጋባዦች በዞኑ እና በከተማ አስተዳደሩ፣ በአባ ገዳዎች፣ በሀደ ሲንቄዎች እንዲሁም በሀገር ሽማግሌዎች አቀባበል ተደርጎላቸዋል። ነገ በሚካሄደው በዚህ ታሪካዊ ኹነት ህብረተሰቡ በነቃ ሁኔታ እንዲሳተፍ አዘጋጆቹ ጥሪ አቅርበዋል።
3 days ago
በአማራ ክልል በሚቀጥሉት 25 ዓመታት ከተሜነት በተሟላ ደረጃ ይስፋፋል - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር)
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአማራ ክልል በሚቀጥሉት 25 ዓመታት ከተሜነት በተሟላ ደረጃ ይስፋፋል አሉ፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሀገራዊ ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ጉዳዮች ዙሪያ ከአሚኮ ጋር ባደረጉት ቆይታ፥ በአማራ ክልል በገጠር ያለው ነዋሪ የመብራት፣ የውሃ፣ የጤና የተለያዩ ጥያቄዎች ምላሽ እንዲያገኝ የሚሰራ መሆኑን ጠቁመዋል።
በዚህም በክልሉ በሚቀጥሉት 25 ዓመታት ከተሜነት በተሟላ ደረጃ ይስፋፋል ብለዋል፡፡
በመስኖ፣ በቴክኖሎጂ፣ ምርታማነትን የማሳደግ ጉዳይ አሁን ካለው ጋር ለውድድር የሚበቃ ነው ብዬ አላስብም ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ አምራች ዘርፉ፣ ኢንዱስትሪው በብዙ ደረጃ ይቀየራል ሲሉ ጠቁመዋል።
የዲጂታል ኢኮኖሚ በኢትዮጵያ ውስጥ በስፋት እንደሚረጋገጥ አንስተዋል።
አሁን ያለው ትውልድ በከፋፋይ፣ በውሸት፣ መሰረት በሌለው ታሪክ ላይ ቆሞ የሚነታረክ መሆኑ አብቅቶ የሚጠቅመውንና የሚፈይደውን የሀገርን ጥቅም ማዕከል ያደረገውን ትርክት ገንብቶ ለጋራ ጥቅም መረባረብ እንዳለበትም አመልክተዋል።
አማራን ብቻ ሳይሆን አካባቢን የሚጠቅም ብልጽግና እናረጋግጣለን፤ ብልጽግናውንም የሚያስተዳድር ትውልድን አብረን እንፈጥራለን ብለዋል።
ይህ ጉዳይ የሁሉንም ርብርብ እንደሚጠይቅ ገልጸው፤ ይህ ትውልድ ስራውን ከሰራ መጪው ትውልድ የተሻለ ህይወት እንደሚኖረውና የአማራም ህዝብ ከዚህ እንደሚጠቀም ተስፋ አደርጋለሁ ነው ያሉት፡፡
FBC
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአማራ ክልል በሚቀጥሉት 25 ዓመታት ከተሜነት በተሟላ ደረጃ ይስፋፋል አሉ፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሀገራዊ ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ጉዳዮች ዙሪያ ከአሚኮ ጋር ባደረጉት ቆይታ፥ በአማራ ክልል በገጠር ያለው ነዋሪ የመብራት፣ የውሃ፣ የጤና የተለያዩ ጥያቄዎች ምላሽ እንዲያገኝ የሚሰራ መሆኑን ጠቁመዋል።
በዚህም በክልሉ በሚቀጥሉት 25 ዓመታት ከተሜነት በተሟላ ደረጃ ይስፋፋል ብለዋል፡፡
በመስኖ፣ በቴክኖሎጂ፣ ምርታማነትን የማሳደግ ጉዳይ አሁን ካለው ጋር ለውድድር የሚበቃ ነው ብዬ አላስብም ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ አምራች ዘርፉ፣ ኢንዱስትሪው በብዙ ደረጃ ይቀየራል ሲሉ ጠቁመዋል።
የዲጂታል ኢኮኖሚ በኢትዮጵያ ውስጥ በስፋት እንደሚረጋገጥ አንስተዋል።
አሁን ያለው ትውልድ በከፋፋይ፣ በውሸት፣ መሰረት በሌለው ታሪክ ላይ ቆሞ የሚነታረክ መሆኑ አብቅቶ የሚጠቅመውንና የሚፈይደውን የሀገርን ጥቅም ማዕከል ያደረገውን ትርክት ገንብቶ ለጋራ ጥቅም መረባረብ እንዳለበትም አመልክተዋል።
አማራን ብቻ ሳይሆን አካባቢን የሚጠቅም ብልጽግና እናረጋግጣለን፤ ብልጽግናውንም የሚያስተዳድር ትውልድን አብረን እንፈጥራለን ብለዋል።
ይህ ጉዳይ የሁሉንም ርብርብ እንደሚጠይቅ ገልጸው፤ ይህ ትውልድ ስራውን ከሰራ መጪው ትውልድ የተሻለ ህይወት እንደሚኖረውና የአማራም ህዝብ ከዚህ እንደሚጠቀም ተስፋ አደርጋለሁ ነው ያሉት፡፡
FBC
4 days ago
ጦርነት ተከፍቶብናል:-ህወሓት‼️
"የትግራይ ህልውና በብልፅግና መቃብር ላይ ይወሰናል" በሚል ስብሰባ ሲያካሂድ የከረመው ህወሓት በምዕራብ ትግራይ ተኩስ ተከፍቶብናል ብሏል።
ሙሉ የመግለጫው ትርጉም👇👇
"የፌደራል መንግሥቱ የትግራይን ሕዝብ ለማጥፋት ሲያካሂድ የቆየውን ሁለንተናዊ ከበባ እና እገዳ፣ በድሮን እና በተላላኪ ታጣቂዎቹ ሲፈጽም የቆየውን ጥቃት ወደ ከፍተኛ ደረጃ በማሳደግ፣ ዛሬ ሐምሌ 25 ቀን 2018 ዓ.ም. ከማለዳው ጀምሮ በምዕራባዊ ትግራይ ዞን በሸረሪ አቅጣጫ ግልጽ ጦርነት ጀምሯል።
የፕሪቶሪያው ስምምነት ከተፈረመ በኋላ እንኳ የትግራይን ሕዝብ ለማንበርከክ እና ለመበታተን ካለው ከፍተኛ ፍላጎት ተነሥቶ የተለያዩ ከበባዎችን፣ እገዳዎችን እና ወታደራዊ ዝግጅቶችን ሲያደርግ ቆይቶ፤ ድጋሚ ትግራይን ለመውረር እና ሕዝቡን ለማጥፋት ተነሳሽነት ወስዶ ጦርነት ከፍቶብናል።
ስለሆነም በሀገር ውስጥ እና በውጭ የምትኖሩ የትግራይ ሕዝብ፣ ሁላችሁም የትግራይ የጸጥታ ኃይሎች፣ ብሔራዊ ኃይሎች እና የትግራይ ታጋዮች፣ የትግራይ ሲቪል ማኅበራት፣ የትግራይ ሃይማኖት ተቋማት እና ሌሎች የሚመለከታችሁ አካላት በሙሉ ብሔራዊ ህልውናችንን ለማረጋገጥ በሚደረገው ፍትሐዊ ትግል "ለብሔራዊ ጥፋት ፈጽሞ አንበረከክም! ብላችሁ ዛሬም እንደ ትናንቱ ተአምራዊ ታሪክ ለመሥራት እንድትዘጋጁ እያቀረብን፤ የተጀመረውን ድጋሚ ወረራ እና ጥፋት የሚመለከቱ የሁኔታዎች እድገት በየጊዜው በሚመለከታቸው አካላት አስፈላጊው ማብራሪያ እና መግለጫ የሚሰጥበት መሆኑን እናስታውቃለን" ብሏል።
Seledadotio
Seledadotio
"የትግራይ ህልውና በብልፅግና መቃብር ላይ ይወሰናል" በሚል ስብሰባ ሲያካሂድ የከረመው ህወሓት በምዕራብ ትግራይ ተኩስ ተከፍቶብናል ብሏል።
ሙሉ የመግለጫው ትርጉም👇👇
"የፌደራል መንግሥቱ የትግራይን ሕዝብ ለማጥፋት ሲያካሂድ የቆየውን ሁለንተናዊ ከበባ እና እገዳ፣ በድሮን እና በተላላኪ ታጣቂዎቹ ሲፈጽም የቆየውን ጥቃት ወደ ከፍተኛ ደረጃ በማሳደግ፣ ዛሬ ሐምሌ 25 ቀን 2018 ዓ.ም. ከማለዳው ጀምሮ በምዕራባዊ ትግራይ ዞን በሸረሪ አቅጣጫ ግልጽ ጦርነት ጀምሯል።
የፕሪቶሪያው ስምምነት ከተፈረመ በኋላ እንኳ የትግራይን ሕዝብ ለማንበርከክ እና ለመበታተን ካለው ከፍተኛ ፍላጎት ተነሥቶ የተለያዩ ከበባዎችን፣ እገዳዎችን እና ወታደራዊ ዝግጅቶችን ሲያደርግ ቆይቶ፤ ድጋሚ ትግራይን ለመውረር እና ሕዝቡን ለማጥፋት ተነሳሽነት ወስዶ ጦርነት ከፍቶብናል።
ስለሆነም በሀገር ውስጥ እና በውጭ የምትኖሩ የትግራይ ሕዝብ፣ ሁላችሁም የትግራይ የጸጥታ ኃይሎች፣ ብሔራዊ ኃይሎች እና የትግራይ ታጋዮች፣ የትግራይ ሲቪል ማኅበራት፣ የትግራይ ሃይማኖት ተቋማት እና ሌሎች የሚመለከታችሁ አካላት በሙሉ ብሔራዊ ህልውናችንን ለማረጋገጥ በሚደረገው ፍትሐዊ ትግል "ለብሔራዊ ጥፋት ፈጽሞ አንበረከክም! ብላችሁ ዛሬም እንደ ትናንቱ ተአምራዊ ታሪክ ለመሥራት እንድትዘጋጁ እያቀረብን፤ የተጀመረውን ድጋሚ ወረራ እና ጥፋት የሚመለከቱ የሁኔታዎች እድገት በየጊዜው በሚመለከታቸው አካላት አስፈላጊው ማብራሪያ እና መግለጫ የሚሰጥበት መሆኑን እናስታውቃለን" ብሏል።
Seledadotio
Seledadotio
4 days ago
ሳውዲ አረቢያን ጨምሮ በርካታ የአረብ ሀገራት በጋዛ የተደረሰውን ስምምነት እንደሚደግፉ ገለጹ
የተለያዩ የአረብ ሀገራት በጋዛ የተደረሰውን ስምምነት በበጎ ሁኔታ እንደሚቀበሉ የገለጹ ሲሆን፣ እስራኤልም ግዴታዎቿን እንድትወጣ ጥሪ አቅርበዋል።
ሳውዲ አረቢያ በጋዛ የተደረሰውን ስምምነት በደስታ እንደምትቀበል ገልጻ፤ እስራኤል ጦሯን ከጋዛ ሙሉ በሙሉ እንድታስወጣ፣ ሰብአዊ እርዳታዎች ያለማቋረጥ እንዲገቡ እና የሰላም እቅዱ ደረጃዎች በሙሉ ተግባራዊ እንዲሆኑ ጠይቃለች።
ኳታር በበኩሏ እስራኤል በስምምነቱ መሠረት ግዴታዎቿን እንድትወጣ እና የተኩስ አቁም የመንገድ ካርታው ቀሪ ምዕራፎች ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ እንዲደረጉ አሳስባለች።
ዮርዳኖስም በተመሳሳይ የእስራኤል ጦር ከጋዛ ግዛት ሙሉ በሙሉ እንዲወጣ፣ ሰብአዊ እርዳታዎች በዘላቂነት እንዲቀርቡ እና የስምምነቱ ቀጣይ ምዕራፍ እንዲተገበር ጥሪዋን አስተላልፋለች።
የኩዌት መንግሥት በበኩሉ የእስራኤል ጦር መውጣትን፣ የእርዳታ አቅርቦት መቀጠልን እና መልሶ የመገንባት ጥረቶችን ጨምሮ የጋዛው ስምምነት ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ እንዲሆን ድጋፉን ገልጿል።
ሀገራቱ ይህን ጥሪ ያቀረቡት በጋዛ ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን እና በጦርነት የደቀቀውን አካባቢ መልሶ ለመገንባት በሚያስችሉ ሁኔታዎች ላይ ትኩረት በማድረግ መሆኑ ተገልጿል።
ልዑል ወልዴ
የተለያዩ የአረብ ሀገራት በጋዛ የተደረሰውን ስምምነት በበጎ ሁኔታ እንደሚቀበሉ የገለጹ ሲሆን፣ እስራኤልም ግዴታዎቿን እንድትወጣ ጥሪ አቅርበዋል።
ሳውዲ አረቢያ በጋዛ የተደረሰውን ስምምነት በደስታ እንደምትቀበል ገልጻ፤ እስራኤል ጦሯን ከጋዛ ሙሉ በሙሉ እንድታስወጣ፣ ሰብአዊ እርዳታዎች ያለማቋረጥ እንዲገቡ እና የሰላም እቅዱ ደረጃዎች በሙሉ ተግባራዊ እንዲሆኑ ጠይቃለች።
ኳታር በበኩሏ እስራኤል በስምምነቱ መሠረት ግዴታዎቿን እንድትወጣ እና የተኩስ አቁም የመንገድ ካርታው ቀሪ ምዕራፎች ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ እንዲደረጉ አሳስባለች።
ዮርዳኖስም በተመሳሳይ የእስራኤል ጦር ከጋዛ ግዛት ሙሉ በሙሉ እንዲወጣ፣ ሰብአዊ እርዳታዎች በዘላቂነት እንዲቀርቡ እና የስምምነቱ ቀጣይ ምዕራፍ እንዲተገበር ጥሪዋን አስተላልፋለች።
የኩዌት መንግሥት በበኩሉ የእስራኤል ጦር መውጣትን፣ የእርዳታ አቅርቦት መቀጠልን እና መልሶ የመገንባት ጥረቶችን ጨምሮ የጋዛው ስምምነት ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ እንዲሆን ድጋፉን ገልጿል።
ሀገራቱ ይህን ጥሪ ያቀረቡት በጋዛ ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን እና በጦርነት የደቀቀውን አካባቢ መልሶ ለመገንባት በሚያስችሉ ሁኔታዎች ላይ ትኩረት በማድረግ መሆኑ ተገልጿል።
ልዑል ወልዴ
4 days ago
#tecno_spark_50
አዲሱ የቴክኖ ስፓርክ 50 የMediaTek Helio G81 ፕሮሰሰር ስለተገጠመለት መዘግየት የሚባል ነገር አይታሰብም፡፡ የተለያዩ ስራዎችን ሲከውኑበት እና ስልክ ሲያወሩበት ቢውሉ ያለምንም መዝግየት ያገለግሎታል፡፡ አዲሱ የቴክኖ ስፓርክ 50 ያለምንም መዘግየት የሚያገለግሎትን ሁነኛ ስልክ ፤ ዛሬ ነገ ሳይሉ የራሶት ያድርጉት። ይገባዎታል!!
#spark50 #spark50series #tecnoai #tecnoet
tecno_et
አዲሱ የቴክኖ ስፓርክ 50 የMediaTek Helio G81 ፕሮሰሰር ስለተገጠመለት መዘግየት የሚባል ነገር አይታሰብም፡፡ የተለያዩ ስራዎችን ሲከውኑበት እና ስልክ ሲያወሩበት ቢውሉ ያለምንም መዝግየት ያገለግሎታል፡፡ አዲሱ የቴክኖ ስፓርክ 50 ያለምንም መዘግየት የሚያገለግሎትን ሁነኛ ስልክ ፤ ዛሬ ነገ ሳይሉ የራሶት ያድርጉት። ይገባዎታል!!
#spark50 #spark50series #tecnoai #tecnoet
tecno_et
4 days ago
የእንጦጦ ሐመረ ኖኅ ቅድስት ኪዳነ ምሕረት አንድነት ገዳም የሚያስገነባውን ሕንፃ
የፕሮጀክቱ ዓላማ
(Project Overview)
የገዳሙ አበው መነኮሳት እና ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ማረፊያ ቤት።
2. ሕንፃው በውስጡ የሚያካታታቸው
(Building Facilities)
* የአበው መነኮሳት እና ሊቃውንት ማረፊያ
* ክርስትና መጠመቂያ ቤት
* ሙዚየም
* የተለያዩ አዳራሾች
* ለቢሮ አገልግሎት የሚሆኑ ክፍሎች
3. የባንክ ሂሳብ ቁጥሮችና መዋጮ ማድረጊያ
(Donation Accounts)
ሀ) የገዳሙ አካውንት
ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፡ 1000003517504
አባይ ባንክ፡ 9841111014325318
አጭር ቁጥር፡ 1612
ለ) የልማት ኮሚቴ አካውንት
ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፡ 1000003780779
አባይ ባንክ፡ 9841011002322017
አጭር ቁጥር፡ 1216
4. ወቅታዊ ሁኔታ
(Current Status)
በስተቀኝ በኩል በሚታዩት ፎቶዎች ላይ እንደሚታየው ሕንፃው አሁን ያለበት የስትራክቸርና የሲቪል ግንባታ ደረጃ ("አሁን ያለበት ደረጃ") ይታያል።
እናታችን ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ሁላችሁንም በበረከቷ ትጎብኛችሁ፤ አሜን!
የፕሮጀክቱ ዓላማ
(Project Overview)
የገዳሙ አበው መነኮሳት እና ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ማረፊያ ቤት።
2. ሕንፃው በውስጡ የሚያካታታቸው
(Building Facilities)
* የአበው መነኮሳት እና ሊቃውንት ማረፊያ
* ክርስትና መጠመቂያ ቤት
* ሙዚየም
* የተለያዩ አዳራሾች
* ለቢሮ አገልግሎት የሚሆኑ ክፍሎች
3. የባንክ ሂሳብ ቁጥሮችና መዋጮ ማድረጊያ
(Donation Accounts)
ሀ) የገዳሙ አካውንት
ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፡ 1000003517504
አባይ ባንክ፡ 9841111014325318
አጭር ቁጥር፡ 1612
ለ) የልማት ኮሚቴ አካውንት
ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፡ 1000003780779
አባይ ባንክ፡ 9841011002322017
አጭር ቁጥር፡ 1216
4. ወቅታዊ ሁኔታ
(Current Status)
በስተቀኝ በኩል በሚታዩት ፎቶዎች ላይ እንደሚታየው ሕንፃው አሁን ያለበት የስትራክቸርና የሲቪል ግንባታ ደረጃ ("አሁን ያለበት ደረጃ") ይታያል።
እናታችን ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ሁላችሁንም በበረከቷ ትጎብኛችሁ፤ አሜን!
4 days ago
«ግሩፕ 26» የተባለው የፈጣን ድጋፍ ኃይሎች አባል የሆነ ወታደራዊ ቡድን ለሱዳን ጦር እጁን ሰጠ
የሱዳን ፈጣን ድጋፍ ኃይሎች (RSF) አባል የሆነው እና «ግሩፕ 26» በመባል የሚታወቀው ወታደራዊ ቡድን በኦምዱርማን አካባቢ ለሱዳን ጦር (SAF) እጁን መስጠቱን፣ አባላቱን እና ወታደራዊ ትጥቆቹን ማስረከቡን የሱዳን ዜና ኤጀንሲ (SUNA) ዘገበ።
ወደ 45 የሚጠጉ ተዋጊዎችን እና መኮንኖችን የያዘው ይህ ቡድን፣ የሱዳን ጦር በቅርቡ በሰሜን ኮርዶፋን ያደረገውን ግስገሳ ተከተሎ ከባራ እና ከሌሎች የአካባቢው ስፍራዎች በመሸሽ የመጣ እንደሆነ ተገልጿል።
ተዋጊዎቹ የውጊያ ተሽከርካሪዎችን እና የተለያዩ የጦር መሣሪያዎችን ጨምሮ ሙሉ ወታደራዊ ትጥቃቸውን ይዘው እጃቸውን መስጠታቸውን ሱና ዘግቧል።
ይህ ክስተት የተፈጸመው የሱዳን ጦር ኤል ኦቤይድን ከዋና ከተማዋ ጋር የሚያገናኙ ስትራቴጂካዊ መስመሮችን ጨምሮ በሰሜን ኮርዶፋን ያለውን ወታደራዊ እንቅስቃሴ ባሰፋበት ወቅት ነው።
Seledadotio
Seledadotio
የሱዳን ፈጣን ድጋፍ ኃይሎች (RSF) አባል የሆነው እና «ግሩፕ 26» በመባል የሚታወቀው ወታደራዊ ቡድን በኦምዱርማን አካባቢ ለሱዳን ጦር (SAF) እጁን መስጠቱን፣ አባላቱን እና ወታደራዊ ትጥቆቹን ማስረከቡን የሱዳን ዜና ኤጀንሲ (SUNA) ዘገበ።
ወደ 45 የሚጠጉ ተዋጊዎችን እና መኮንኖችን የያዘው ይህ ቡድን፣ የሱዳን ጦር በቅርቡ በሰሜን ኮርዶፋን ያደረገውን ግስገሳ ተከተሎ ከባራ እና ከሌሎች የአካባቢው ስፍራዎች በመሸሽ የመጣ እንደሆነ ተገልጿል።
ተዋጊዎቹ የውጊያ ተሽከርካሪዎችን እና የተለያዩ የጦር መሣሪያዎችን ጨምሮ ሙሉ ወታደራዊ ትጥቃቸውን ይዘው እጃቸውን መስጠታቸውን ሱና ዘግቧል።
ይህ ክስተት የተፈጸመው የሱዳን ጦር ኤል ኦቤይድን ከዋና ከተማዋ ጋር የሚያገናኙ ስትራቴጂካዊ መስመሮችን ጨምሮ በሰሜን ኮርዶፋን ያለውን ወታደራዊ እንቅስቃሴ ባሰፋበት ወቅት ነው።
Seledadotio
Seledadotio
5 days ago
ሲ.አይ.ኤ እና ሞሳድ የኢራን አዲሱን የበላይ መሪ ሙጅተባ ኻመነኢን ለማግኘት የሚያደርጉት ጥረት ትኩረት ስቧል
#ዓለም | የብሪታንያው The Times ጋዜጣ የደህንነት ምንጮችን ጠቅሶ እንደዘገበው፣ የአሜሪካው ሲ.አይ.ኤ (CIA) እና የእስራኤሉ ሞሳድ (Mossad) የኢራን አዲሱ የበላይ መሪ ሙጅተባ ኻመነኢ የት እንዳሉ ለማረጋገጥ እና ሁኔታቸውን ለመከታተል የስለላ ጥረታቸውን አጠናክረዋል።
ሪፖርቱ እንደሚለው፣ ሙጅተባ ኻመነኢ ከአባታቸው ሞት በኋላ የኢራንን ከፍተኛ አመራር ቢረከቡም፣ በአደባባይ አልታዩም፤ ስልክ፣ ኮምፒውተር ወይም ሌሎች የኤሌክትሮኒክስ መገናኛ ዘዴዎችን እንደማይጠቀሙም ይገለጻል። በዚህ ምክንያት በሳተላይት እና በሳይበር መንገድ የሚደረገው ክትትል ውጤታማ እንዳልሆነ ተነግሯል።
በዚህ ሁኔታ የምዕራባውያን የደህንነት ተቋማት ትኩረታቸውን ከኤሌክትሮኒክስ ስለላ ወደ Human Intelligence (HUMINT) ወይም በሰዎች በኩል የሚሰበሰብ መረጃ ላይ ማዞራቸው ተዘግቧል። አንዳንድ የቀድሞ የሞሳድ ባለስልጣናት እንደሚሉት፣ ሙጅተባ መልእክቶችን በብዙ ደረጃ በተደራጁ ተላላኪዎች እንደሚያስተላልፉ ይገመታል።
ሆኖም እስካሁን ድረስ ሙጅተባ ኻመነኢ የት እንዳሉ፣ በምን ዓይነት የጤና ሁኔታ እንዳሉ ወይም በቀጥታ አገሪቱን እየመሩ መሆናቸው በገለልተኛ ምንጮች አልተረጋገጠም። የአሜሪካና የእስራኤል ባለሥልጣናትም እነዚህን ሪፖርቶች በይፋ አላረጋገጡም።
አንዳንድ ሚዲያዎች ሙጅተባ ኻመነኢ በሕይወት ስለመኖራቸው ወይም ስለ ምትክ ሰዎች (body doubles) የሚያነሱት ጥርጣሬ መኖሩን ቢዘግቡም፣ እነዚህ አባባሎች በገለልተኛ ማስረጃ ያልተረጋገጡ ግምቶች መሆናቸውን የዓለም አቀፍ የዜና ተቋማት ያስገነዝባሉ።
ተንታኞች እንደሚሉት፣ ሙጅተባ ኻመነኢ በሕዝብ ፊት አለመታየታቸው በኢራን የሥልጣን አወቃቀር፣ በአብዮታዊ ዘብ (IRGC) ያለው ተጽዕኖ እና በቀጣናው የደህንነት ሁኔታ ላይ የተለያዩ ጥያቄዎችን እያስነሳ ነው። ነገር ግን ከስለላ ሪፖርቶች ባሻገር የተረጋገጠ ኦፊሴላዊ መረጃ አሁንም አልቀረበም።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#ዓለም | የብሪታንያው The Times ጋዜጣ የደህንነት ምንጮችን ጠቅሶ እንደዘገበው፣ የአሜሪካው ሲ.አይ.ኤ (CIA) እና የእስራኤሉ ሞሳድ (Mossad) የኢራን አዲሱ የበላይ መሪ ሙጅተባ ኻመነኢ የት እንዳሉ ለማረጋገጥ እና ሁኔታቸውን ለመከታተል የስለላ ጥረታቸውን አጠናክረዋል።
ሪፖርቱ እንደሚለው፣ ሙጅተባ ኻመነኢ ከአባታቸው ሞት በኋላ የኢራንን ከፍተኛ አመራር ቢረከቡም፣ በአደባባይ አልታዩም፤ ስልክ፣ ኮምፒውተር ወይም ሌሎች የኤሌክትሮኒክስ መገናኛ ዘዴዎችን እንደማይጠቀሙም ይገለጻል። በዚህ ምክንያት በሳተላይት እና በሳይበር መንገድ የሚደረገው ክትትል ውጤታማ እንዳልሆነ ተነግሯል።
በዚህ ሁኔታ የምዕራባውያን የደህንነት ተቋማት ትኩረታቸውን ከኤሌክትሮኒክስ ስለላ ወደ Human Intelligence (HUMINT) ወይም በሰዎች በኩል የሚሰበሰብ መረጃ ላይ ማዞራቸው ተዘግቧል። አንዳንድ የቀድሞ የሞሳድ ባለስልጣናት እንደሚሉት፣ ሙጅተባ መልእክቶችን በብዙ ደረጃ በተደራጁ ተላላኪዎች እንደሚያስተላልፉ ይገመታል።
ሆኖም እስካሁን ድረስ ሙጅተባ ኻመነኢ የት እንዳሉ፣ በምን ዓይነት የጤና ሁኔታ እንዳሉ ወይም በቀጥታ አገሪቱን እየመሩ መሆናቸው በገለልተኛ ምንጮች አልተረጋገጠም። የአሜሪካና የእስራኤል ባለሥልጣናትም እነዚህን ሪፖርቶች በይፋ አላረጋገጡም።
አንዳንድ ሚዲያዎች ሙጅተባ ኻመነኢ በሕይወት ስለመኖራቸው ወይም ስለ ምትክ ሰዎች (body doubles) የሚያነሱት ጥርጣሬ መኖሩን ቢዘግቡም፣ እነዚህ አባባሎች በገለልተኛ ማስረጃ ያልተረጋገጡ ግምቶች መሆናቸውን የዓለም አቀፍ የዜና ተቋማት ያስገነዝባሉ።
ተንታኞች እንደሚሉት፣ ሙጅተባ ኻመነኢ በሕዝብ ፊት አለመታየታቸው በኢራን የሥልጣን አወቃቀር፣ በአብዮታዊ ዘብ (IRGC) ያለው ተጽዕኖ እና በቀጣናው የደህንነት ሁኔታ ላይ የተለያዩ ጥያቄዎችን እያስነሳ ነው። ነገር ግን ከስለላ ሪፖርቶች ባሻገር የተረጋገጠ ኦፊሴላዊ መረጃ አሁንም አልቀረበም።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
5 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) 'እግረኛው' በተሰኘው የዩቲዩብ ቻናል የተለያዩ ግለሰቦችን ቃለ ምልልስ በማድረግ የሚታወቀው ጋዜጠኛ ተክለሀይማኖት አዳነ፣ እንዲሁም የሀገር መከላከያ ሰራዊት የደንብ ልብስ በመልበስ አከራካሪ መልዕክቶችን ሲያስተላልፍ የነበረው አበባየሁ ደሜ (አለማየሁ) በፌዴራል ፖሊስ ቁጥጥር ስር ዋሉ።
የፌዴራል ፖሊስ ጋዜጠኛ ተክለሀይማኖትን ዛሬ በፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አንደኛ የወንጀል ችሎት ያቀረበው ሲሆን፣ "ሀሰተኛ መረጃ በማሰራጨትና ፍትህን ለማዛባት በመሞከር" ወንጀል እንደጠረጠረው ለችሎቱ አስታውቋል። ፍርድ ቤቱም የፖሊስን የክስ መዝገብ ከመረመረ በኋላ፣ የቀረበለትን የጊዜ ቀጠሮ ጥያቄ በመቀበል ለሐምሌ 28 ቀን 2018 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል። በመሆኑም አቶ ተክለሀይማኖት እስከ ቀጠሮው ዕለት ድረስ በማረሚያ ቤት በእስር የሚቆይ ይሆናል።
የጋዜጠኛው በቁጥጥር ስር መዋል መነሻ ምክንያት በውል ባይታወቅም፣ በቅርቡ ከ'ፊንቴክ' (Fintech) የመኪና ማጭበርበር ጉዳይ ጋር በተያያዘ ክስ ከተመሰረተባቸው አርቲስቶች ጋር ያደረገውን ቃለ ምልልስ በሚዲያው በሁለት ክፍሎች ማሰራጨቱ ይታወሳል። በተጨማሪም የሀገር መከላከያ ሰራዊት ልብስ ለብሶ ከቀረበው ግለሰብ ጋር ያደረገው አነጋጋሪ ቃለ ምልልስ ለዚህ እስር መንስኤ ሊሆን እንደሚችል ቢገመትም፣ ጉዳዩ ከነዚሁ ስርጭቶች ጋር ይያያዝ አይያያዝ ዘ-ሐበሻ ማረጋገጥ አልቻለም።
በተያያዘ ዜና፣ በጋዜጠኛው ሚዲያ ላይ ቃለ ምልልስ የሰጠው ግለሰብም በቁጥጥር ስር መዋሉ ተገልጿል። የሀገር መከላከያ ሰራዊት አልባሳትን ያለአግባብ በመጠቀም በየማህበራዊ ሚዲያው የአንድነትና የፍቅር ሀሳብ ከማስተላለፍ ይልቅ የመከፋፈል ንግግሮችን እና አላስፈላጊ መልእክቶችን ሲያሰራጭ የነበረው አበባየሁ ደሜ በፖሊስ ተይዟል።
የፌዴራል ፖሊስ ጋዜጠኛ ተክለሀይማኖትን ዛሬ በፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አንደኛ የወንጀል ችሎት ያቀረበው ሲሆን፣ "ሀሰተኛ መረጃ በማሰራጨትና ፍትህን ለማዛባት በመሞከር" ወንጀል እንደጠረጠረው ለችሎቱ አስታውቋል። ፍርድ ቤቱም የፖሊስን የክስ መዝገብ ከመረመረ በኋላ፣ የቀረበለትን የጊዜ ቀጠሮ ጥያቄ በመቀበል ለሐምሌ 28 ቀን 2018 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል። በመሆኑም አቶ ተክለሀይማኖት እስከ ቀጠሮው ዕለት ድረስ በማረሚያ ቤት በእስር የሚቆይ ይሆናል።
የጋዜጠኛው በቁጥጥር ስር መዋል መነሻ ምክንያት በውል ባይታወቅም፣ በቅርቡ ከ'ፊንቴክ' (Fintech) የመኪና ማጭበርበር ጉዳይ ጋር በተያያዘ ክስ ከተመሰረተባቸው አርቲስቶች ጋር ያደረገውን ቃለ ምልልስ በሚዲያው በሁለት ክፍሎች ማሰራጨቱ ይታወሳል። በተጨማሪም የሀገር መከላከያ ሰራዊት ልብስ ለብሶ ከቀረበው ግለሰብ ጋር ያደረገው አነጋጋሪ ቃለ ምልልስ ለዚህ እስር መንስኤ ሊሆን እንደሚችል ቢገመትም፣ ጉዳዩ ከነዚሁ ስርጭቶች ጋር ይያያዝ አይያያዝ ዘ-ሐበሻ ማረጋገጥ አልቻለም።
በተያያዘ ዜና፣ በጋዜጠኛው ሚዲያ ላይ ቃለ ምልልስ የሰጠው ግለሰብም በቁጥጥር ስር መዋሉ ተገልጿል። የሀገር መከላከያ ሰራዊት አልባሳትን ያለአግባብ በመጠቀም በየማህበራዊ ሚዲያው የአንድነትና የፍቅር ሀሳብ ከማስተላለፍ ይልቅ የመከፋፈል ንግግሮችን እና አላስፈላጊ መልእክቶችን ሲያሰራጭ የነበረው አበባየሁ ደሜ በፖሊስ ተይዟል።
Sponsored by
Surafel
5 days ago
ሼፍ ሄኖክ ዘርይሁን የምስራቅ አፍሪካ ሼፎች ማህበር ፕሬዝዳንት ሆነው ተመረጡ
📌 ኢትዮጵያ የ2027ቱን አህጉራዊ ፌስቲቫል እንድታዘጋጅ ተወሰነ
#fastmereja I የኢትዮጵያ ሼፎች ማህበር ፕሬዝዳንት ሼፍ ሄኖክ ዘርይሁን የምስራቅ አፍሪካ ሼፎች ማህበር ፕሬዝዳንት ሆነው ተመረጡ። በደቡብ አፍሪካ እና በስዋቲኒ በተካሄደው የ2026 የአፍሪካ ሼፎች ፌስቲቫል ላይ ኢትዮጵያን ወክለው የተሳተፉት ሼፍ ሄኖክ ይህን ከፍተኛ ኃላፊነት ከመጨበጣቸውም በላይ፣ ሀገራችን ኢትዮጵያ የ2027ቱን የመላው አፍሪካ የሼፎች ፌስቲቫል በጋራ እንድታዘጋጅ ውሳኔ ተላላፏል።
በደቡብ አፍሪካ እና በስዋቲኒ አስተናጋጅነት በተካሄደው በዚህ አህጉራዊ መድረክ የአፍሪካ የምግብ ግብአቶች፣ የአዘገጃጀት እና የአመጋገብ ታሪክ በሰፊው የተዳሰሰ ሲሆን፣ ዘርፉን የሚያጎለብቱ የተለያዩ አለም አቀፋዊ ስልጠናዎችም ተሰጥተዋል። ኢትዮጵያ እጅግ በርካታ የተፈጥሮ የምግብ ግብአቶች እና ሀብታም የአመጋገብ ባህል ያላት ሀገር እንደመሆኗ መጠን፣ ይህ ታሪካዊ አጋጣሚ ሀገሪቱ ያላትን እምቅ ሀብት ለመላው አለም ለማስተዋወቅና በገበያ ላይ በማቅረብ ከዘርፉ ማግኘት የሚገባትን ኢኮኖሚያዊ ጥቅም እንድታገኝ ትልቅ መንገድ የሚከፍት መሆኑ ተገልጿል።
ይህንን ተከትሎ ኢትዮጵያ የ2027ቱን አህጉራዊ የሼፎች ፌስቲቫል እንድታዘጋጅ መመረጧ በምግብ ቱሪዝም እና በባህል ልውውጥ ዘርፍ አዲስ ምዕራፍ የሚከፍት ሲሆን፣ የሀገሪቱን ገጽታ በበጎ መልኩ በመገንባት ረገድ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ይታመናል።
📌 ኢትዮጵያ የ2027ቱን አህጉራዊ ፌስቲቫል እንድታዘጋጅ ተወሰነ
#fastmereja I የኢትዮጵያ ሼፎች ማህበር ፕሬዝዳንት ሼፍ ሄኖክ ዘርይሁን የምስራቅ አፍሪካ ሼፎች ማህበር ፕሬዝዳንት ሆነው ተመረጡ። በደቡብ አፍሪካ እና በስዋቲኒ በተካሄደው የ2026 የአፍሪካ ሼፎች ፌስቲቫል ላይ ኢትዮጵያን ወክለው የተሳተፉት ሼፍ ሄኖክ ይህን ከፍተኛ ኃላፊነት ከመጨበጣቸውም በላይ፣ ሀገራችን ኢትዮጵያ የ2027ቱን የመላው አፍሪካ የሼፎች ፌስቲቫል በጋራ እንድታዘጋጅ ውሳኔ ተላላፏል።
በደቡብ አፍሪካ እና በስዋቲኒ አስተናጋጅነት በተካሄደው በዚህ አህጉራዊ መድረክ የአፍሪካ የምግብ ግብአቶች፣ የአዘገጃጀት እና የአመጋገብ ታሪክ በሰፊው የተዳሰሰ ሲሆን፣ ዘርፉን የሚያጎለብቱ የተለያዩ አለም አቀፋዊ ስልጠናዎችም ተሰጥተዋል። ኢትዮጵያ እጅግ በርካታ የተፈጥሮ የምግብ ግብአቶች እና ሀብታም የአመጋገብ ባህል ያላት ሀገር እንደመሆኗ መጠን፣ ይህ ታሪካዊ አጋጣሚ ሀገሪቱ ያላትን እምቅ ሀብት ለመላው አለም ለማስተዋወቅና በገበያ ላይ በማቅረብ ከዘርፉ ማግኘት የሚገባትን ኢኮኖሚያዊ ጥቅም እንድታገኝ ትልቅ መንገድ የሚከፍት መሆኑ ተገልጿል።
ይህንን ተከትሎ ኢትዮጵያ የ2027ቱን አህጉራዊ የሼፎች ፌስቲቫል እንድታዘጋጅ መመረጧ በምግብ ቱሪዝም እና በባህል ልውውጥ ዘርፍ አዲስ ምዕራፍ የሚከፍት ሲሆን፣ የሀገሪቱን ገጽታ በበጎ መልኩ በመገንባት ረገድ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ይታመናል።
5 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ አክሲዮን ማህበር ላለፉት ሁለት የውድድር ዘመናት በክለቦች የተጫዋቾች እና የቴክኒክ አባላት የደመወዝ ክፍያ ላይ ጥሎት የነበረውን ዓመታዊ የወጪ ጣሪያ ሙሉ በሙሉ ማንሳቱን አስታውቋል።
ባለፈው የውድድር ዘመን እያንዳንዱ ክለብ በዓመት ለደመወዝ ማውጣት የሚችለው ከፍተኛው የገንዘብ መጠን 70 ሚሊዮን ብር እንዲሆን ተወስኖ ነበር። ይህ የገንዘብ ጣሪያ አሰራሩ ለመጀመሪያ ጊዜ ሲተገበር ከነበረው 50 ሚሊዮን ብር ከፍ ተደርጎ የተተገበረ ቢሆንም፣ አዲሱ የሊጉ ውሳኔ ግን ክለቦች ለ2026/27 የውድድር ዘመን ያለምንም የገንዘብ ገደብ የደመወዝ በጀታቸውን በራሳቸው እንዲወስኑ ሙሉ ነፃነት ይሰጣቸዋል።
ይህ የገንዘብ ጣሪያ በአንድ ተጫዋች ደመወዝ ላይ ሳይሆን ክለቦች በአጠቃላይ ለደመወዝ በሚያወጡት ወጪ ላይ የተጣለ ሲሆን፣ ዋነኛ ዓላማውም እያሻቀበ የመጣውን የደመወዝ ወጪ ለመቆጣጠር እና የተለያየ የፋይናንስ አቅም ባላቸው ክለቦች መካከል ያለውን የፋይናንስ ፉክክር ለማመጣጠን ነበር። ጣሪያው መነሳቱ በክረምቱ የተጫዋቾች ዝውውር እና የውል ድርድር ላይ ትልቅ ለውጥ እንደሚያመጣ ይጠበቃል፤ ምክንያቱም ክለቦች ከዚህ በኋላ ዓመታዊ የደመወዝ ወጪያቸውን ከ70 ሚሊዮን ብር በታች ለማድረግ አይገደዱም።
ይህ ውሳኔ የተላለፈው አብዛኛዎቹ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ክለቦች አሁንም ለህልውናቸው በክልል መንግስታት፣ በከተማ አስተዳደሮች፣ በመንግስት ተቋማት እና በልማት ድርጅቶች ዓመታዊ በጀት ላይ ጥገኛ በሆኑበት ወቅት ነው። ከስፖንሰርሺፕ፣ ከቴሌቪዥን ስርጭት መብት፣ ከቲኬት ሽያጭ፣ ከማልያ ሽያጭ እና ከመሳሰሉት የንግድ እንቅስቃሴዎች የሚገኘው ገቢ አሁንም በመላው ሊጉ እጅግ አነስተኛ ሆኖ ቀጥሏል። የበርካታ ክለቦች ዋነኛ የፋይናንስ ምንጭ አመታዊ የበጀት ድልድል ሲሆን፣ በርካቶቹ የራሳቸው ስታዲየም፣ ቋሚ የመለማመጃ ሜዳ ወይም ቋሚ ገቢ የሚያስገኝ የንግድ ተቋም የላቸውም።
የስፖርት ተንታኙ ፈይሰል ዘኪር የደመወዝ ወጪን መጨመር ብቻውን የኢትዮጵያን እግር ኳስ መዋቅራዊ ችግር እንደማይፈታው ያስገነዝባል። "ብዙ ገንዘብ ማውጣት ምንም አዲስ ነገር አያመጣም፤ ይልቁንም ይኸው ገንዘብ ለክለቦች ስታዲየም ለመገንባት እና ትልቅ አቅም ያላቸውን ወጣት ተጫዋቾች ለማፍራት መዋል ነበረበት" በማለት ተችቷል። ክለቦች ወጪያቸውን ከማሳደጋቸው በፊት ዘላቂ የገቢ ምንጭ መፍጠር ላይ ሊያተኩሩ እንደሚገባም አሳስቧል። አክሎም "በጀት አመዳደቡ የአጭር ጊዜ ውጤት ላይ ብቻ ያተኮረ ነው፤ ለዚህም ነው አንድ ክለብ በአንድ የውድድር ዘመን ከላይ አጠናቆ፣ በሚቀጥለው ዓመት በጀቱ ሲያልቅ ወደ ታች የሚወርደው" ሲል የችግሩን ስር-መሰረት አብራርቷል።
በአህጉር አቀፍ ደረጃ የተለያዩ የአፍሪካ ሊጎች በክለብ ወጪ እና በተጫዋቾች ክፍያ ላይ የተለያየ አሰራር አላቸው። ለምሳሌ ጋና የክለቦችን አጠቃላይ ወጪ ከመገደብ ይልቅ ለተጫዋቾች የሚከፈል አነስተኛ የደመወዝ እርከን በማውጣት ተጫዋቾችን ትጠብቃለች። ደቡብ አፍሪካ ደግሞ ምንም ዓይነት የደመወዝ ጣሪያ ሳታስቀምጥ ክለቦች በስፖንሰር እና በቴሌቪዥን መብት በሚያገኙት ገቢ በነጻነት ይደራደራሉ። በአውሮፓ እግር ኳስ ማህበር (UEFA) በኩል ደግሞ የክለቦችን ወጪ ከሚያገኙት ገቢ ጋር የሚያስተሳስር የፋይናንስ ህግ ይተገበራል።
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የተነሳውን የደመወዝ ጣሪያ በሌላ ከገቢ ጋር በተገናኘ የፋይናንስ ህግ ወይም የፋይናንስ ሪፖርት አቀራረብ ስርዓት ስለመተካቱ እስካሁን ያሳወቀው ነገር የለም። የጣሪያው መነሳት ለክለቦች በዝውውር ገበያው ላይ ሰፊ ነፃነት ቢሰጥም፣ የደመወዝ ክፍያ ግዴታዎችን ማክበር እና የፋይናንስ አስተዳደር ኃላፊነትን ግን ሙሉ በሙሉ በእያንዳንዱ ክለብ ትከሻ ላይ ጥሎታል ያስብላል።
ባለፈው የውድድር ዘመን እያንዳንዱ ክለብ በዓመት ለደመወዝ ማውጣት የሚችለው ከፍተኛው የገንዘብ መጠን 70 ሚሊዮን ብር እንዲሆን ተወስኖ ነበር። ይህ የገንዘብ ጣሪያ አሰራሩ ለመጀመሪያ ጊዜ ሲተገበር ከነበረው 50 ሚሊዮን ብር ከፍ ተደርጎ የተተገበረ ቢሆንም፣ አዲሱ የሊጉ ውሳኔ ግን ክለቦች ለ2026/27 የውድድር ዘመን ያለምንም የገንዘብ ገደብ የደመወዝ በጀታቸውን በራሳቸው እንዲወስኑ ሙሉ ነፃነት ይሰጣቸዋል።
ይህ የገንዘብ ጣሪያ በአንድ ተጫዋች ደመወዝ ላይ ሳይሆን ክለቦች በአጠቃላይ ለደመወዝ በሚያወጡት ወጪ ላይ የተጣለ ሲሆን፣ ዋነኛ ዓላማውም እያሻቀበ የመጣውን የደመወዝ ወጪ ለመቆጣጠር እና የተለያየ የፋይናንስ አቅም ባላቸው ክለቦች መካከል ያለውን የፋይናንስ ፉክክር ለማመጣጠን ነበር። ጣሪያው መነሳቱ በክረምቱ የተጫዋቾች ዝውውር እና የውል ድርድር ላይ ትልቅ ለውጥ እንደሚያመጣ ይጠበቃል፤ ምክንያቱም ክለቦች ከዚህ በኋላ ዓመታዊ የደመወዝ ወጪያቸውን ከ70 ሚሊዮን ብር በታች ለማድረግ አይገደዱም።
ይህ ውሳኔ የተላለፈው አብዛኛዎቹ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ክለቦች አሁንም ለህልውናቸው በክልል መንግስታት፣ በከተማ አስተዳደሮች፣ በመንግስት ተቋማት እና በልማት ድርጅቶች ዓመታዊ በጀት ላይ ጥገኛ በሆኑበት ወቅት ነው። ከስፖንሰርሺፕ፣ ከቴሌቪዥን ስርጭት መብት፣ ከቲኬት ሽያጭ፣ ከማልያ ሽያጭ እና ከመሳሰሉት የንግድ እንቅስቃሴዎች የሚገኘው ገቢ አሁንም በመላው ሊጉ እጅግ አነስተኛ ሆኖ ቀጥሏል። የበርካታ ክለቦች ዋነኛ የፋይናንስ ምንጭ አመታዊ የበጀት ድልድል ሲሆን፣ በርካቶቹ የራሳቸው ስታዲየም፣ ቋሚ የመለማመጃ ሜዳ ወይም ቋሚ ገቢ የሚያስገኝ የንግድ ተቋም የላቸውም።
የስፖርት ተንታኙ ፈይሰል ዘኪር የደመወዝ ወጪን መጨመር ብቻውን የኢትዮጵያን እግር ኳስ መዋቅራዊ ችግር እንደማይፈታው ያስገነዝባል። "ብዙ ገንዘብ ማውጣት ምንም አዲስ ነገር አያመጣም፤ ይልቁንም ይኸው ገንዘብ ለክለቦች ስታዲየም ለመገንባት እና ትልቅ አቅም ያላቸውን ወጣት ተጫዋቾች ለማፍራት መዋል ነበረበት" በማለት ተችቷል። ክለቦች ወጪያቸውን ከማሳደጋቸው በፊት ዘላቂ የገቢ ምንጭ መፍጠር ላይ ሊያተኩሩ እንደሚገባም አሳስቧል። አክሎም "በጀት አመዳደቡ የአጭር ጊዜ ውጤት ላይ ብቻ ያተኮረ ነው፤ ለዚህም ነው አንድ ክለብ በአንድ የውድድር ዘመን ከላይ አጠናቆ፣ በሚቀጥለው ዓመት በጀቱ ሲያልቅ ወደ ታች የሚወርደው" ሲል የችግሩን ስር-መሰረት አብራርቷል።
በአህጉር አቀፍ ደረጃ የተለያዩ የአፍሪካ ሊጎች በክለብ ወጪ እና በተጫዋቾች ክፍያ ላይ የተለያየ አሰራር አላቸው። ለምሳሌ ጋና የክለቦችን አጠቃላይ ወጪ ከመገደብ ይልቅ ለተጫዋቾች የሚከፈል አነስተኛ የደመወዝ እርከን በማውጣት ተጫዋቾችን ትጠብቃለች። ደቡብ አፍሪካ ደግሞ ምንም ዓይነት የደመወዝ ጣሪያ ሳታስቀምጥ ክለቦች በስፖንሰር እና በቴሌቪዥን መብት በሚያገኙት ገቢ በነጻነት ይደራደራሉ። በአውሮፓ እግር ኳስ ማህበር (UEFA) በኩል ደግሞ የክለቦችን ወጪ ከሚያገኙት ገቢ ጋር የሚያስተሳስር የፋይናንስ ህግ ይተገበራል።
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የተነሳውን የደመወዝ ጣሪያ በሌላ ከገቢ ጋር በተገናኘ የፋይናንስ ህግ ወይም የፋይናንስ ሪፖርት አቀራረብ ስርዓት ስለመተካቱ እስካሁን ያሳወቀው ነገር የለም። የጣሪያው መነሳት ለክለቦች በዝውውር ገበያው ላይ ሰፊ ነፃነት ቢሰጥም፣ የደመወዝ ክፍያ ግዴታዎችን ማክበር እና የፋይናንስ አስተዳደር ኃላፊነትን ግን ሙሉ በሙሉ በእያንዳንዱ ክለብ ትከሻ ላይ ጥሎታል ያስብላል።
6 days ago
በጅማ ዞን ከ1,800 በላይ የልማት ፕሮጀክቶች በ5.1 ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ ተገነቡ
#ethiopia | በጅማ ዞን በ2018 በጀት ዓመት ከ5.1 ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ 1,876 የልማት ፕሮጀክቶች መገንባታቸውን የዞኑ አስተዳዳሪ አቶ ቲጃኒ ናስር ገልጸዋል።
አስተዳዳሪው ይህን ያስታወቁት በጅማ ዞን ሰቃ ጨቆርሳ ወረዳ የተገነቡ የተለያዩ የመሠረተ ልማት ፕሮጀክቶች በይፋ በተመረቁበት ሥነ ሥርዓት ላይ ነው።
ለአገልግሎት ከተከፈቱት ፕሮጀክቶች መካከል መንገዶች፣ ድልድዮች፣ የሁለተኛ ትውልድ ጤና ኬላ፣ የገበያ ማዕከል፣ የግብርና ግብዓት ማከማቻ መጋዘን፣ የወረዳ አስተዳደር ሕንፃ እና ሌሎች ማህበራዊ መሠረተ ልማቶች ይገኙበታል።
አቶ ቲጃኒ ናስር እንደገለጹት፣ የህብረተሰቡን የመሠረተ ልማት ፍላጎት ለማሟላት ፕሮጀክቶች በፍጥነትና በጥራት እንዲገነቡ ትኩረት ተሰጥቶ ተሠርቷል።
በመንግሥትና በህዝብ ትብብር የተገነቡት እነዚህ ፕሮጀክቶች የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ ለማጠናከር ከፍተኛ አስተዋፅኦ እንደሚያበረክቱም ገልጸዋል።
የሰቃ ጨቆርሳ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ አብዱልከሪም አባራያ በበኩላቸው፣ በወረዳው ከ800 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ ግንባታቸው ከተጀመሩ 33 ፕሮጀክቶች ውስጥ 23ቱ ተጠናቀው ለአገልግሎት መከፈታቸውን ገልጸው፣ ቀሪዎቹም በአጭር ጊዜ ውስጥ ተጠናቀው ለህብረተሰቡ ጥቅም እንደሚውሉ አስታውቀዋል።
የአካባቢው ነዋሪ አቶ መሀመድ ዘይን ተማም በበኩላቸው፣ በወረዳው የተከናወኑ የመሠረተ ልማት ሥራዎች የህብረተሰቡን የልማት ጥያቄ በመመለስ የኑሮ ሁኔታን እያሻሻሉ መሆናቸውን ገልጸዋል።
በተመሳሳይ የዶዩ ቃጨማ ቀበሌ ነዋሪ አቶ አብዱላሂ አባ ጀበል፣ በአካባቢው የተገነባው የግብርና ግብዓት ማከማቻ መጋዘን ከዚህ ቀደም ግብዓቶችን ለማግኘት ወደ አጎራባች ወረዳዎች በመጓዝ የሚባክነውን ጊዜና ወጪ እንዳስቀረላቸው ገልጸዋል።
የፕሮጀክቶቹ መጠናቀቅ በዞኑ የትራንስፖርት፣ የጤና፣ የንግድና የግብርና አገልግሎቶችን ተደራሽነት በማሳደግ የአካባቢውን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ እንቅስቃሴ የበለጠ እንደሚያነቃቃ ይጠበቃል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#ethiopia | በጅማ ዞን በ2018 በጀት ዓመት ከ5.1 ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ 1,876 የልማት ፕሮጀክቶች መገንባታቸውን የዞኑ አስተዳዳሪ አቶ ቲጃኒ ናስር ገልጸዋል።
አስተዳዳሪው ይህን ያስታወቁት በጅማ ዞን ሰቃ ጨቆርሳ ወረዳ የተገነቡ የተለያዩ የመሠረተ ልማት ፕሮጀክቶች በይፋ በተመረቁበት ሥነ ሥርዓት ላይ ነው።
ለአገልግሎት ከተከፈቱት ፕሮጀክቶች መካከል መንገዶች፣ ድልድዮች፣ የሁለተኛ ትውልድ ጤና ኬላ፣ የገበያ ማዕከል፣ የግብርና ግብዓት ማከማቻ መጋዘን፣ የወረዳ አስተዳደር ሕንፃ እና ሌሎች ማህበራዊ መሠረተ ልማቶች ይገኙበታል።
አቶ ቲጃኒ ናስር እንደገለጹት፣ የህብረተሰቡን የመሠረተ ልማት ፍላጎት ለማሟላት ፕሮጀክቶች በፍጥነትና በጥራት እንዲገነቡ ትኩረት ተሰጥቶ ተሠርቷል።
በመንግሥትና በህዝብ ትብብር የተገነቡት እነዚህ ፕሮጀክቶች የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ ለማጠናከር ከፍተኛ አስተዋፅኦ እንደሚያበረክቱም ገልጸዋል።
የሰቃ ጨቆርሳ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ አብዱልከሪም አባራያ በበኩላቸው፣ በወረዳው ከ800 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ ግንባታቸው ከተጀመሩ 33 ፕሮጀክቶች ውስጥ 23ቱ ተጠናቀው ለአገልግሎት መከፈታቸውን ገልጸው፣ ቀሪዎቹም በአጭር ጊዜ ውስጥ ተጠናቀው ለህብረተሰቡ ጥቅም እንደሚውሉ አስታውቀዋል።
የአካባቢው ነዋሪ አቶ መሀመድ ዘይን ተማም በበኩላቸው፣ በወረዳው የተከናወኑ የመሠረተ ልማት ሥራዎች የህብረተሰቡን የልማት ጥያቄ በመመለስ የኑሮ ሁኔታን እያሻሻሉ መሆናቸውን ገልጸዋል።
በተመሳሳይ የዶዩ ቃጨማ ቀበሌ ነዋሪ አቶ አብዱላሂ አባ ጀበል፣ በአካባቢው የተገነባው የግብርና ግብዓት ማከማቻ መጋዘን ከዚህ ቀደም ግብዓቶችን ለማግኘት ወደ አጎራባች ወረዳዎች በመጓዝ የሚባክነውን ጊዜና ወጪ እንዳስቀረላቸው ገልጸዋል።
የፕሮጀክቶቹ መጠናቀቅ በዞኑ የትራንስፖርት፣ የጤና፣ የንግድና የግብርና አገልግሎቶችን ተደራሽነት በማሳደግ የአካባቢውን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ እንቅስቃሴ የበለጠ እንደሚያነቃቃ ይጠበቃል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
6 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ህገ-መንግስት ከጸደቀ 30 ዓመታት ቢቆጠሩም፣ ሀገሪቱ አሁንም የሰዎችን ህይወት ከሚቀጥፉ፣ ማህበረሰብን ከሚያፈናቅሉ እና የህዝብን አመኔታ ከሚሸረሽሩ ተደጋጋሚ ግጭቶች መላቀቅ አልቻለችም። አብዛኛዎቹ ሰዎች ለእነዚህ ችግሮች የብሔር ወይም የፖለቲካ ፉክክርን በዋነኛነት ቢወቅሱም፣ የፖለቲካ ትንታኔዎች ግን ዋነኛው እና ስር የሰደደው ችግር የፌደራል እና የክልል መንግስታት የጸጥታ ኃላፊነት ድንበር በህገ-መንግስቱ ላይ በግልጽ አለመቀመጡ መሆኑን ያመላክታሉ።
ይህ ግልጽነት የጎደለው አሰራር "የተበታተነ ሉዓላዊነት" ፈጥሯል። ይህም ማለት የተለያዩ የመንግስት እርከኖች በተደራረበ ህጋዊ ስልጣን እና እርስ በርስ በሚፎካከር ፖለቲካዊ ፍላጎት የጸጥታ ኃይልን ያዛሉ። በዚህም ምክንያት የፌደራል እና የክልል የጸጥታ መዋቅሮች ተደጋግፈው ከመስራት ይልቅ፣ አንዳንዴ በትይዩ አልያም በፉክክር መንፈስ ሲንቀሳቀሱ ይታያሉ፤ ይህም ግጭትን ለመከላከል የሚደረገውን ጥረት አወሳስቦታል።
የዚህ አጣብቂኝ መነሻ ያለው እ.ኤ.አ. በ1995 በጸደቀው የኢትዮጵያ ህገ-መንግስት ውስጥ ነው። ህገ-መንግስቱ የሀገር መከላከያ እና የፌደራል ፖሊስን ኃላፊነት ለፌደራል መንግስቱ በአንቀጽ 51(6) ስር ሲሰጥ፣ በሌላ በኩል ደግሞ ክልሎች የራሳቸውን ፖሊስ ኃይል እንዲያቋቁሙ እና ጸጥታ እንዲያስከብሩ በአንቀጽ 52(2)(g) ላይ ስልጣን ይሰጣቸዋል። ይህ ድንጋጌ የክልሎችን ራስን በራስ የማስተዳደር መብት እና የሀገርን አንድነት ለማመጣጠን የታለመ ቢሆንም፣ የክልል የፖሊስ ስልጣን የት ላይ ያበቃል የፌደራል የጸጥታ ኃላፊነትስ የት ይጀምራል ለሚለው መሰረታዊ ጥያቄ ምላሽ ሳይሰጥ ቀርቷል።
በዚህም ምክንያት ሁለት ተቋማዊ ድክመቶች ተፈጥረዋል። የመጀመሪያው፣ ክልሎች የተሰጣቸውን የፖሊስ ኃይል የማቋቋም መብት በመጠቀም ከመደበኛ የፖሊስ ግዳጅ ባለፈ ወታደራዊ ቅርጽ እና ትጥቅ ያላቸውን የክልል ልዩ ኃይሎችን ማቋቋማቸው ነው። ሁለተኛው ደግሞ፣ በክልሎች መካከል የሚነሱ የድንበር እና የማንነት ጥያቄዎችን የሚፈታ ጠንካራ ተቋማዊ አሰራር ባለመኖሩ የክልል ፖሊስ ተቋማት የፖለቲካው አካል በመሆን ግጭቶችን ከማብረድ ይልቅ ተሳታፊ ወደ መሆን መሸጋገራቸው ነው።
ህገ-መንግስታዊ ክፍተት ብቻውን ብጥብጥ አያመጣም። ነገር ግን ፖለቲከኞች የጸጥታ ኃላፊነቶች በተደራረቡበት ስርዓት ውስጥ ሲንቀሳቀሱ አደገኛ ይሆናል። በኢትዮጵያ፣ አንዱ የመንግስት እርከን ለራሱ ደህንነት ሲል የሚወስደው ራስን የመከላከል እርምጃ፣ በሌላው ወገን እንደ ትንኮሳ እና ለጥቃት እንደመዘጋጀት ይቆጠራል።
ይህ ተለዋዋጭ ሁኔታ በሚያዝያ 2015 ዓ.ም. የፌደራል መንግስት የክልል ልዩ ኃይሎችን መልሶ ለማደራጀት በወሰደው እርምጃ ወቅት በግልጽ ታይቷል። መንግስት እርምጃውን የተዋሃደ ሀገራዊ የጸጥታ መዋቅር ለመገንባት ያለመ መሆኑን ቢገልጽም፣ በተለይም በአማራ ክልል ከፍተኛ ፖለቲካዊ ተቃውሞን እና ቀጣይነት ያለውን ግጭት አስከትሏል። ይህ የሚያሳየው፣ የክልል መንግስታት የጸጥታ ተቋሞቻቸውን እንደ ህገ-መንግስታዊ የራስ ገዝ አስተዳደር መገለጫ አድርገው በሚያዩበት ፌደራላዊ ስርዓት ውስጥ፣ ኃይልን ማዕከላዊ ለማድረግ የሚደረግ ማንኛውም ሙከራ እንደ ፖለቲካዊ ጣልቃ ገብነት እንደሚቆጠር ነው።
መዋቅራዊ መፍትሄዎች፡ ኃይልን ብቻ ሳይሆን ህጉን ማስተካከል
የኢትዮጵያን ተደጋጋሚ የጸጥታ ቀውሶች በዘላቂነት ለመፍታት የተለያዩ መዋቅራዊ ማሻሻያዎችን ማድረግ የግድ ይላል። በቅድሚያ በአንቀጽ 51 እና በአንቀጽ 52 መካከል ያለውን የፌደራል እና የክልል የጸጥታ ኃላፊነቶች ግንኙነት በግልጽ በማብራራት የፌደራል መንግስት በምን ዓይነት ሁኔታዎች ውስጥ ጣልቃ መግባት እንዳለበት ህጋዊ ድንበር ሊቀመጥ ይገባል። በተጨማሪም የክልልን ራስን በራስ የማስተዳደር መብት በማይጋፋ መልኩ፣ መረጃ የሚለዋወጡበት እና ግጭቶች ወደ ጦርነት ከማምራታቸው በፊት የሚፈቱበት ቋሚ የፌደራል እና የክልል የጸጥታ ማስተባበሪያ መዋቅር መገንባት ያስፈልጋል።
በሌላ በኩል የፖሊስ ተቋማት ከፖለቲካ ወገንተኝነት የጸዱ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ እና በፖለቲካ የተነሳሱ የጸጥታ ጥሰቶችን የሚመረምር ገለልተኛ የቁጥጥር አካል በማቋቋም ተቋማዊ ተጠያቂነትን ማረጋገጥ ወሳኝ እርምጃ ነው። እንዲሁም የክልል ፖሊሶች ለክልል ፖለቲካዊ ፍላጎቶች ሳይሆን ለህገ-መንግስቱ እና ለህግ የበላይነት ታማኝ የሚሆኑበትን የጋራ ስልጠና እና ኦፕሬሽናል መርሆች በመተግበር የጋራ ፕሮፌሽናል አስተምህሮ ማዳበር ይገባል።
የኢትዮጵያ ተደጋጋሚ የጸጥታ ቀውሶች የሚያሳዩት "ህገ-መንግስታዊ ንድፍ ልክ እንደ ፖለቲካዊ አመራር ሁሉ እጅግ ወሳኝ መሆኑን" ነው። ዘላቂ ሰላም ጊዜያዊ ተኩስ አቁምን ወይም ወቅታዊ የጸጥታ ዘመቻዎችን ብቻ ተመርኩዞ ሊመጣ አይችልም። የኢትዮጵያ ማዕከላዊ ጥያቄ የጸጥታ ማሻሻያ ያስፈልጋል ወይ የሚለው ሳይሆን፣ ማሻሻያው የችግሩን ውጫዊ ምልክቶች ብቻ ሳይሆን ተቋማዊ እና ህገ-መንግስታዊ ስር-መሰረቱን ይፈታል ወይ የሚለው ነው።
ይህ ግልጽነት የጎደለው አሰራር "የተበታተነ ሉዓላዊነት" ፈጥሯል። ይህም ማለት የተለያዩ የመንግስት እርከኖች በተደራረበ ህጋዊ ስልጣን እና እርስ በርስ በሚፎካከር ፖለቲካዊ ፍላጎት የጸጥታ ኃይልን ያዛሉ። በዚህም ምክንያት የፌደራል እና የክልል የጸጥታ መዋቅሮች ተደጋግፈው ከመስራት ይልቅ፣ አንዳንዴ በትይዩ አልያም በፉክክር መንፈስ ሲንቀሳቀሱ ይታያሉ፤ ይህም ግጭትን ለመከላከል የሚደረገውን ጥረት አወሳስቦታል።
የዚህ አጣብቂኝ መነሻ ያለው እ.ኤ.አ. በ1995 በጸደቀው የኢትዮጵያ ህገ-መንግስት ውስጥ ነው። ህገ-መንግስቱ የሀገር መከላከያ እና የፌደራል ፖሊስን ኃላፊነት ለፌደራል መንግስቱ በአንቀጽ 51(6) ስር ሲሰጥ፣ በሌላ በኩል ደግሞ ክልሎች የራሳቸውን ፖሊስ ኃይል እንዲያቋቁሙ እና ጸጥታ እንዲያስከብሩ በአንቀጽ 52(2)(g) ላይ ስልጣን ይሰጣቸዋል። ይህ ድንጋጌ የክልሎችን ራስን በራስ የማስተዳደር መብት እና የሀገርን አንድነት ለማመጣጠን የታለመ ቢሆንም፣ የክልል የፖሊስ ስልጣን የት ላይ ያበቃል የፌደራል የጸጥታ ኃላፊነትስ የት ይጀምራል ለሚለው መሰረታዊ ጥያቄ ምላሽ ሳይሰጥ ቀርቷል።
በዚህም ምክንያት ሁለት ተቋማዊ ድክመቶች ተፈጥረዋል። የመጀመሪያው፣ ክልሎች የተሰጣቸውን የፖሊስ ኃይል የማቋቋም መብት በመጠቀም ከመደበኛ የፖሊስ ግዳጅ ባለፈ ወታደራዊ ቅርጽ እና ትጥቅ ያላቸውን የክልል ልዩ ኃይሎችን ማቋቋማቸው ነው። ሁለተኛው ደግሞ፣ በክልሎች መካከል የሚነሱ የድንበር እና የማንነት ጥያቄዎችን የሚፈታ ጠንካራ ተቋማዊ አሰራር ባለመኖሩ የክልል ፖሊስ ተቋማት የፖለቲካው አካል በመሆን ግጭቶችን ከማብረድ ይልቅ ተሳታፊ ወደ መሆን መሸጋገራቸው ነው።
ህገ-መንግስታዊ ክፍተት ብቻውን ብጥብጥ አያመጣም። ነገር ግን ፖለቲከኞች የጸጥታ ኃላፊነቶች በተደራረቡበት ስርዓት ውስጥ ሲንቀሳቀሱ አደገኛ ይሆናል። በኢትዮጵያ፣ አንዱ የመንግስት እርከን ለራሱ ደህንነት ሲል የሚወስደው ራስን የመከላከል እርምጃ፣ በሌላው ወገን እንደ ትንኮሳ እና ለጥቃት እንደመዘጋጀት ይቆጠራል።
ይህ ተለዋዋጭ ሁኔታ በሚያዝያ 2015 ዓ.ም. የፌደራል መንግስት የክልል ልዩ ኃይሎችን መልሶ ለማደራጀት በወሰደው እርምጃ ወቅት በግልጽ ታይቷል። መንግስት እርምጃውን የተዋሃደ ሀገራዊ የጸጥታ መዋቅር ለመገንባት ያለመ መሆኑን ቢገልጽም፣ በተለይም በአማራ ክልል ከፍተኛ ፖለቲካዊ ተቃውሞን እና ቀጣይነት ያለውን ግጭት አስከትሏል። ይህ የሚያሳየው፣ የክልል መንግስታት የጸጥታ ተቋሞቻቸውን እንደ ህገ-መንግስታዊ የራስ ገዝ አስተዳደር መገለጫ አድርገው በሚያዩበት ፌደራላዊ ስርዓት ውስጥ፣ ኃይልን ማዕከላዊ ለማድረግ የሚደረግ ማንኛውም ሙከራ እንደ ፖለቲካዊ ጣልቃ ገብነት እንደሚቆጠር ነው።
መዋቅራዊ መፍትሄዎች፡ ኃይልን ብቻ ሳይሆን ህጉን ማስተካከል
የኢትዮጵያን ተደጋጋሚ የጸጥታ ቀውሶች በዘላቂነት ለመፍታት የተለያዩ መዋቅራዊ ማሻሻያዎችን ማድረግ የግድ ይላል። በቅድሚያ በአንቀጽ 51 እና በአንቀጽ 52 መካከል ያለውን የፌደራል እና የክልል የጸጥታ ኃላፊነቶች ግንኙነት በግልጽ በማብራራት የፌደራል መንግስት በምን ዓይነት ሁኔታዎች ውስጥ ጣልቃ መግባት እንዳለበት ህጋዊ ድንበር ሊቀመጥ ይገባል። በተጨማሪም የክልልን ራስን በራስ የማስተዳደር መብት በማይጋፋ መልኩ፣ መረጃ የሚለዋወጡበት እና ግጭቶች ወደ ጦርነት ከማምራታቸው በፊት የሚፈቱበት ቋሚ የፌደራል እና የክልል የጸጥታ ማስተባበሪያ መዋቅር መገንባት ያስፈልጋል።
በሌላ በኩል የፖሊስ ተቋማት ከፖለቲካ ወገንተኝነት የጸዱ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ እና በፖለቲካ የተነሳሱ የጸጥታ ጥሰቶችን የሚመረምር ገለልተኛ የቁጥጥር አካል በማቋቋም ተቋማዊ ተጠያቂነትን ማረጋገጥ ወሳኝ እርምጃ ነው። እንዲሁም የክልል ፖሊሶች ለክልል ፖለቲካዊ ፍላጎቶች ሳይሆን ለህገ-መንግስቱ እና ለህግ የበላይነት ታማኝ የሚሆኑበትን የጋራ ስልጠና እና ኦፕሬሽናል መርሆች በመተግበር የጋራ ፕሮፌሽናል አስተምህሮ ማዳበር ይገባል።
የኢትዮጵያ ተደጋጋሚ የጸጥታ ቀውሶች የሚያሳዩት "ህገ-መንግስታዊ ንድፍ ልክ እንደ ፖለቲካዊ አመራር ሁሉ እጅግ ወሳኝ መሆኑን" ነው። ዘላቂ ሰላም ጊዜያዊ ተኩስ አቁምን ወይም ወቅታዊ የጸጥታ ዘመቻዎችን ብቻ ተመርኩዞ ሊመጣ አይችልም። የኢትዮጵያ ማዕከላዊ ጥያቄ የጸጥታ ማሻሻያ ያስፈልጋል ወይ የሚለው ሳይሆን፣ ማሻሻያው የችግሩን ውጫዊ ምልክቶች ብቻ ሳይሆን ተቋማዊ እና ህገ-መንግስታዊ ስር-መሰረቱን ይፈታል ወይ የሚለው ነው።
Sponsored by
Surafel
6 days ago
በሀዋሳ ከተማ በረዶ ቀላቅሎ በጣለ ከባድ ዝናብ የአንድ ሰው ህይወት አለፈ
👉አደጋው በ1ሰው ላይ ከባድ እና በ8 ሰዎች ላይ ቀላል ጉዳት ኡድርሷል
በሀዋሳ ከተማ ትናንት ምሽት በተከሰተው ያልተለመደ ኃይለኛ ንፋስ እና በረዶ ቀላቅሎ በጣለ ዝናብ ምክንያት የአንድ ሰው ህይወቱ ማለፉን የከተማዋ ሰላምና ፀጥታ ቢሮ አስታውቋል።በአደጋው አንድ ሰው ላይ ከባድ የአካል ጉዳት ሲደርስ በ8 ሰዎች ደግሞ ቀላል ጉዳት እንደደረሰባቸው ተገልጿል።
የሀዋሳ ከተማ ሰላምና ፀጥታ ቢሮ የመምሪያ ኃላፊ አቶ ወንድሙ ቶርባ ለብስራት ሬዲዮ እንደተናገሩት በአደጋው በርካታ ቤቶች ጣሪያዎች በኃይለኛው ንፋስ ተነስተው በመውደቃቸው በሰዎችና በንብረት ላይ ጉዳት ደርሷል።በተጨማሪም የኮንክሪት የኤሌክትሪክና የቴሌ ፖሎች በመውደቃቸው በከተማዋ በባህል አዳራሽ ምሥራቅ እና መሀል ክፍለ ከተማዎች አካባቢ የኃይል መቋረጥ መከሰቱን ገልጸዋል።
በአደጋው ሁለት መኪኖችና አንድ ባጃጅ ላይ የዛፍ ቅርንጫፎች በመውደቃቸው የመስታወት መሰበር ጉዳት ቢደርስም ከባድ ጉዳት እንዳልደረሰባቸው ተጠቁሟል። በባጃጁ ውስጥ የነበሩ ሰዎች ከአደጋው በፊት ወጥተው በመጠለላቸው ከጉዳት መትረፋቸው ተገልጿል።በከተማዋ የተሰሩት የኮሪደር ልማት ላይ የደረሰ ጉዳት ስለመኖሩ ለአቶ ወንድሙ ብስራት ሬዲዮ ጥያቄ ያነሳ ሲሆን አዳዲስ የተሰሩ የኮሪደር ልማት ስራዎች እና ቦዮች ወይም ካናሎች ጎርፍ በቀላሉ እንዲፈስ ስለረዱ ከጎርፍ ጋር ተያይዞ የሚመጣውን አደጋ በከፍተኛ ሁኔታ ቀናንሰውታል በኮሪደር ልማቱ ላይ የደረሰ የጎርፍ ጉዳት የለም ሲሉ ተናግረዋል።
የከተማ አስተዳደሩና የተለያዩ አካላት በማድረግ ባሉት የመስክ ምልከታ መሠረት አስቸኳይ ድጋፍ ለሚያስፈልጋቸው ወገኖች ድጋፍ ለማድረግ ሥራዎች እየተጀመሩ መሆኑ ተገልጿል።አደጋው ለ8 ደቂቃ ያህል አጭር ጊዜ ቢቆይም የንፋሱና የበረዶው መጠን ከፍተኛ እንደነበር ተጠቁሟል። ህብረተሰቡም የቅድመ ማስጠንቀቂያ መረጃዎችን በመከታተል ጥንቃቄ እንዲያደርግ ጥሪ ቀርቧል።
Seledadotio
Seledadotio
👉አደጋው በ1ሰው ላይ ከባድ እና በ8 ሰዎች ላይ ቀላል ጉዳት ኡድርሷል
በሀዋሳ ከተማ ትናንት ምሽት በተከሰተው ያልተለመደ ኃይለኛ ንፋስ እና በረዶ ቀላቅሎ በጣለ ዝናብ ምክንያት የአንድ ሰው ህይወቱ ማለፉን የከተማዋ ሰላምና ፀጥታ ቢሮ አስታውቋል።በአደጋው አንድ ሰው ላይ ከባድ የአካል ጉዳት ሲደርስ በ8 ሰዎች ደግሞ ቀላል ጉዳት እንደደረሰባቸው ተገልጿል።
የሀዋሳ ከተማ ሰላምና ፀጥታ ቢሮ የመምሪያ ኃላፊ አቶ ወንድሙ ቶርባ ለብስራት ሬዲዮ እንደተናገሩት በአደጋው በርካታ ቤቶች ጣሪያዎች በኃይለኛው ንፋስ ተነስተው በመውደቃቸው በሰዎችና በንብረት ላይ ጉዳት ደርሷል።በተጨማሪም የኮንክሪት የኤሌክትሪክና የቴሌ ፖሎች በመውደቃቸው በከተማዋ በባህል አዳራሽ ምሥራቅ እና መሀል ክፍለ ከተማዎች አካባቢ የኃይል መቋረጥ መከሰቱን ገልጸዋል።
በአደጋው ሁለት መኪኖችና አንድ ባጃጅ ላይ የዛፍ ቅርንጫፎች በመውደቃቸው የመስታወት መሰበር ጉዳት ቢደርስም ከባድ ጉዳት እንዳልደረሰባቸው ተጠቁሟል። በባጃጁ ውስጥ የነበሩ ሰዎች ከአደጋው በፊት ወጥተው በመጠለላቸው ከጉዳት መትረፋቸው ተገልጿል።በከተማዋ የተሰሩት የኮሪደር ልማት ላይ የደረሰ ጉዳት ስለመኖሩ ለአቶ ወንድሙ ብስራት ሬዲዮ ጥያቄ ያነሳ ሲሆን አዳዲስ የተሰሩ የኮሪደር ልማት ስራዎች እና ቦዮች ወይም ካናሎች ጎርፍ በቀላሉ እንዲፈስ ስለረዱ ከጎርፍ ጋር ተያይዞ የሚመጣውን አደጋ በከፍተኛ ሁኔታ ቀናንሰውታል በኮሪደር ልማቱ ላይ የደረሰ የጎርፍ ጉዳት የለም ሲሉ ተናግረዋል።
የከተማ አስተዳደሩና የተለያዩ አካላት በማድረግ ባሉት የመስክ ምልከታ መሠረት አስቸኳይ ድጋፍ ለሚያስፈልጋቸው ወገኖች ድጋፍ ለማድረግ ሥራዎች እየተጀመሩ መሆኑ ተገልጿል።አደጋው ለ8 ደቂቃ ያህል አጭር ጊዜ ቢቆይም የንፋሱና የበረዶው መጠን ከፍተኛ እንደነበር ተጠቁሟል። ህብረተሰቡም የቅድመ ማስጠንቀቂያ መረጃዎችን በመከታተል ጥንቃቄ እንዲያደርግ ጥሪ ቀርቧል።
Seledadotio
Seledadotio
6 days ago
የመከረ ቤቱን አጠናከረ
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 22፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ሀገራችን በአንድ ግዙፍ የታሪክ ምዕራፍ እጥፋት ላይ ትገኛለች፡፡ በታሪኳ ለመጀመሪያ ጊዜ የውስጥ ጉዳዮቿን የሀገር ልጆች ቁጭ ብለው ተመካክረው ሀገር ሊያጸኑ ተሰባስበዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የምክክሩን አስፈላጊነት በተመለከተ ሲናገሩ፣ "ለልጆቿ ኩራት የሆነች፣ ተስፋ ያላት ምድር ለማድረግ አንድንችል ምክክሩ በእጅጉ ያስፈልጋል" ነው ያሉት፡፡
ኢትዮጵያ በርካታ ብሔር ብሔረሰቦች የሚኖሩባት ባለ ብዝሃ ባህል፣ ብዝሃ ታሪክ፣ ብዝሃ ማህበረ ኢኮኖሚ ሀገር እንደመሆኗ በዘመናት ጉዞዋ የልማት፣ የአስተዳደራዊ እና ሌሎች አለመግባባቶች እንደሚኖሩ ይጠበቃል፡፡
የእነዚህን በህዝቦች መካል የሚስተዋሉ ልዩነቶች አለመግባባቶችና ጥያቄዎች በዘላቂነት በመፍታት ህብረ ብሔራዊ አንድነቷ የተጠበቀ፣ የበለጸገችና የታፈረች ኢትዮጵያን ለትውልድ ለማስተላለፍ ምክክሩ እጅግ ያስፈልጋል።
ብሔራዊ ምክክሩ የታለመለትን ግብ እንዲመታ እና ሀገር እንድትጸና ለማድረግ የሁሉምን ህብረተሰብ ክፍሎች ያካተተ እና ያሳተፈ እንዲሆን ተደርጓል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የምክክር ሂደቱ፣ "በፖለቲካ ልሂቃን መካከል የሚደረግ ብቻ ሳይሆን የሁሉንም የህብረተሰብ ክፍሎች ተሳትፎ ያገናዘበ፣ በኢትዮጵያውያን የተመራ ሀገር በቀል መፍትሄዎችን ለማፍለቅ ታልሞ የሚከናወን ይሆናል" ባሉት መሰረት የሀገር ሽማግሌዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ ምሁራን፣ ሴቶች፣ ወጣቶች፣ ሠራተኞች፣ አካል ጉዳተኞች፣ እንዲሁም ተፈናቃዮች እንዲሳተፉ ተደርጓል።
የተለያዩ የዘርፉ ምሁራን በምክክርና ውይይት ሂደት የአካታችነት እና አሳታፊነትን ፋይዳ ያሰምሩበታል፡፡ በስዊዝፒስ የድርድር ፕሮግራም ኃላፊ የሆኑት ዴቪድ ላንዝ የአንድን ሀገር መሰረታዊ ማንነትና የአስተዳደር ስርዓት ለመወያየት የሚያስችል ሁሉን አቀፍ አሰራር ከሌለ፣ ከዚያ በኋላ የሚደረጉ ማናቸውም ውሳኔዎች ወይም ተቋማዊ ማሻሻያዎች በአሸዋ ላይ እንደተገነባ ቤት ይሆናሉ ይላሉ፡፡
ኢትዮጵያ ሀገር በቀል የሆኑ በዘመናት ተሞክረው እና ተፈትነው በውጤታማነት የዘለቁ የልዩነትና የግጭት መፍቻ ስርዓቶች ባለቤት እንደመሆኗ አሁን እየተካሄደ ያለው የምክክር ጉባኤ የእነዚህ እሴቶች አዲስ ምዕራፍ መገለጫ ተደርጎ ይወሰዳል፡፡
ምክክሩ ሁሉም ሃሳቡን የሚገልፅበት፣ የሌሎች ጥያቄዎችና ቅሬታዎች የሚደምጥበት፣ በጋራ መፍትሄ የሚፈለግበትና የጋራ መግባባት ላይ የሚደረስበት በመሆኑ ውጤቱም ዘላቂና ሀገርን የሚያጸና ነው፡፡
በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ እና በአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር መላው ኢትዮጵያውያን በአንድ ዜማ ተግባብተው ታሪክ እንደሰሩ ሁሉ በሀገራዊ መግባባትና ሀገር መፅናት ጉዳይም ተመሳሳይ ድል የመቀዳጀት ጉዞ ላይ ናቸው።
ይህ ለአፍሪካውያን ብሎም ለዓለም ተምሳሌት ሊሆን የሚችል የኢትጵያውያን፣ በኢትዮጵያውያን ለኢትዮጵያውያን የተዘጋጀ ታሪካዊ መድረክ የበለጸገች ህብረ ብሔራዊ ኢትዮጵያን ለትውልድ ለማስተላለፍ ፅኑ መሰረት ይጥላል።
የምክክር ሂደቱ በስኬት እስኪጠናቀቅ፣ ኢትዮጵያውያን ከሊቅ እስከ ደቂቅ የሚጠበቅባቸውን ሚና ሊወጡ ይገባል፡፡
በቴዎድሮስ ሳህለ
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 22፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ሀገራችን በአንድ ግዙፍ የታሪክ ምዕራፍ እጥፋት ላይ ትገኛለች፡፡ በታሪኳ ለመጀመሪያ ጊዜ የውስጥ ጉዳዮቿን የሀገር ልጆች ቁጭ ብለው ተመካክረው ሀገር ሊያጸኑ ተሰባስበዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የምክክሩን አስፈላጊነት በተመለከተ ሲናገሩ፣ "ለልጆቿ ኩራት የሆነች፣ ተስፋ ያላት ምድር ለማድረግ አንድንችል ምክክሩ በእጅጉ ያስፈልጋል" ነው ያሉት፡፡
ኢትዮጵያ በርካታ ብሔር ብሔረሰቦች የሚኖሩባት ባለ ብዝሃ ባህል፣ ብዝሃ ታሪክ፣ ብዝሃ ማህበረ ኢኮኖሚ ሀገር እንደመሆኗ በዘመናት ጉዞዋ የልማት፣ የአስተዳደራዊ እና ሌሎች አለመግባባቶች እንደሚኖሩ ይጠበቃል፡፡
የእነዚህን በህዝቦች መካል የሚስተዋሉ ልዩነቶች አለመግባባቶችና ጥያቄዎች በዘላቂነት በመፍታት ህብረ ብሔራዊ አንድነቷ የተጠበቀ፣ የበለጸገችና የታፈረች ኢትዮጵያን ለትውልድ ለማስተላለፍ ምክክሩ እጅግ ያስፈልጋል።
ብሔራዊ ምክክሩ የታለመለትን ግብ እንዲመታ እና ሀገር እንድትጸና ለማድረግ የሁሉምን ህብረተሰብ ክፍሎች ያካተተ እና ያሳተፈ እንዲሆን ተደርጓል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የምክክር ሂደቱ፣ "በፖለቲካ ልሂቃን መካከል የሚደረግ ብቻ ሳይሆን የሁሉንም የህብረተሰብ ክፍሎች ተሳትፎ ያገናዘበ፣ በኢትዮጵያውያን የተመራ ሀገር በቀል መፍትሄዎችን ለማፍለቅ ታልሞ የሚከናወን ይሆናል" ባሉት መሰረት የሀገር ሽማግሌዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ ምሁራን፣ ሴቶች፣ ወጣቶች፣ ሠራተኞች፣ አካል ጉዳተኞች፣ እንዲሁም ተፈናቃዮች እንዲሳተፉ ተደርጓል።
የተለያዩ የዘርፉ ምሁራን በምክክርና ውይይት ሂደት የአካታችነት እና አሳታፊነትን ፋይዳ ያሰምሩበታል፡፡ በስዊዝፒስ የድርድር ፕሮግራም ኃላፊ የሆኑት ዴቪድ ላንዝ የአንድን ሀገር መሰረታዊ ማንነትና የአስተዳደር ስርዓት ለመወያየት የሚያስችል ሁሉን አቀፍ አሰራር ከሌለ፣ ከዚያ በኋላ የሚደረጉ ማናቸውም ውሳኔዎች ወይም ተቋማዊ ማሻሻያዎች በአሸዋ ላይ እንደተገነባ ቤት ይሆናሉ ይላሉ፡፡
ኢትዮጵያ ሀገር በቀል የሆኑ በዘመናት ተሞክረው እና ተፈትነው በውጤታማነት የዘለቁ የልዩነትና የግጭት መፍቻ ስርዓቶች ባለቤት እንደመሆኗ አሁን እየተካሄደ ያለው የምክክር ጉባኤ የእነዚህ እሴቶች አዲስ ምዕራፍ መገለጫ ተደርጎ ይወሰዳል፡፡
ምክክሩ ሁሉም ሃሳቡን የሚገልፅበት፣ የሌሎች ጥያቄዎችና ቅሬታዎች የሚደምጥበት፣ በጋራ መፍትሄ የሚፈለግበትና የጋራ መግባባት ላይ የሚደረስበት በመሆኑ ውጤቱም ዘላቂና ሀገርን የሚያጸና ነው፡፡
በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ እና በአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር መላው ኢትዮጵያውያን በአንድ ዜማ ተግባብተው ታሪክ እንደሰሩ ሁሉ በሀገራዊ መግባባትና ሀገር መፅናት ጉዳይም ተመሳሳይ ድል የመቀዳጀት ጉዞ ላይ ናቸው።
ይህ ለአፍሪካውያን ብሎም ለዓለም ተምሳሌት ሊሆን የሚችል የኢትጵያውያን፣ በኢትዮጵያውያን ለኢትዮጵያውያን የተዘጋጀ ታሪካዊ መድረክ የበለጸገች ህብረ ብሔራዊ ኢትዮጵያን ለትውልድ ለማስተላለፍ ፅኑ መሰረት ይጥላል።
የምክክር ሂደቱ በስኬት እስኪጠናቀቅ፣ ኢትዮጵያውያን ከሊቅ እስከ ደቂቅ የሚጠበቅባቸውን ሚና ሊወጡ ይገባል፡፡
በቴዎድሮስ ሳህለ
7 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) በስዊድን ጎተንበርግ ከተማ እየተካሄደ በሚገኘው የ'ጎቲያ ካፕ' የዓለም የወጣቶች እግር ኳስ ውድድር ላይ ለመሳተፍ ካቀኑት የኢትዮጵያ ቡድኖች መካከል፣ 20 የሚሆኑ የአንድ ቡድን ተጫዋቾች እና አጃቢ አዋቂዎች የውድድሩ ማጠቃለያ ዕለት ባልታሰበ ሁኔታ መሰወራቸው ተገልጿል። ይህ ክስተት በስፖርቱ ሽፋን በራሳቸው ፍቃድ የተፈጸመ ህገ-ወጥ ስደት (illegal migration) ሊሆን እንደሚችል የስዊድን ፖሊስ አስታውቋል።
ከ77 ሀገራት የተውጣጡ ቡድኖች በተሳተፉበት በዚህ ውድድር ኢትዮጵያ በአራት ቡድኖች ተወክላ ነበር። ሆኖም የፍጻሜው ውድድር በሚካሄድበት ዕለት የተጫዋቾቹ ማረፊያ የነበረው ትምህርት ቤት አስተናጋጆች፣ አባላቱ እቃቸውን ጠቅልለው መጥፋታቸውን ደርሰውበታል። የጎቲያ ካፕ የፕሬስ ቃል አቀባይ ፍሬድሪክ ቤክማን፣ አዘጋጁ ኮሚቴ ከቡድኑ ጋር ጥሩ ግንኙነት ስለነበረው ድርጊቱ እንዳስገረማቸው ገልጸው፣ ለጥንቃቄ ሲባል ለፖሊስ ሪፖርት ማድረጋቸውን ተናግረዋል። ውድድሩ ከተጠናቀቀ አስር ቀናት ቢያልፉም፣ የቡድኑ አባላት እስካሁን ወደ ኢትዮጵያ አልተመለሱም።
አዘጋጆቹ ከቡድኑ አስተባባሪ በደረሳቸው የኢሜል መልእክት "የተፈጠረው የመግባባት ችግር ነው" የሚል ማስተባበያ ቢሰጥም፣ ተጫዋቾቹ የት እንዳሉ ግን ምንም ዓይነት ፍንጭ አልተሰጠም። የስዊድን ፖሊስ የጠፉ ሰዎችን የመፈለግ ክፍል ኃላፊ ኤሊኖር ሃልዲን እንደገለጹት፣ ከዚህ በፊት በውድድሩ ታሪክ ጥቂት ሰዎች የመጥፋት አጋጣሚ ቢኖርም፣ በአንድ ጊዜ 20 ሰዎች ሲሰወሩ ግን ይህ የመጀመሪያው ነው።
ፖሊስ ከስደተኞች ኤጀንሲ እና ከድንበር ተቆጣጣሪዎች ጋር በመተባበር ፍለጋውን የቀጠለ ሲሆን፣ ድርጊቱ በሰው አዘዋዋሪዎች የተፈጸመ ሳይሆን አባላቱ አስቀድመው ያቀዱት ስደት መሆኑን መረጃዎች ያመለክታሉ።
ይህ ክስተት ዓለም አቀፍ ስፖርታዊ መድረኮች ላልተገባ የስደት ዓላማ መጠቀሚያ እየሆኑ መምጣታቸውን የሚያሳይ አሳሳቢ አጋጣሚ ሆኗል። ታዳጊ አትሌቶች እና አጃቢዎቻቸው ሀገራቸውን ወክለው በሄዱበት የውድድር መድረክ ላይ መሰወራቸው፣ በሀገራት መካከል ያለውን እምነት ከመፈተኑም በላይ፤ በቀጣይ ሌሎች ወጣት ኢትዮጵያውያን ስፖርተኞች ዓለም አቀፍ የውድድር ዕድሎችን እንዳያገኙ እና የቪዛ ክልከላ እንዲያጋጥማቸው ሊያደርግ የሚችል አደገኛ አዝማሚያ መሆኑ የጉዳዩን አሳሳቢነት ያጎላዋል።
የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ባወጣው መግለጫ፤ "ዓመታዊው የጎቲያ ካፕ ውድድር ላይ ለመካፈል ወደ ስዊድን ያመሩ ታዳጊዎች እና የቡድን አባላት በስዊድን መጥፋታቸውን አስመልክቶ የተለያዩ መረጃዎች እየወጡ ይገኛሉ። በጉዳዩ ዙርያ ምላሽ ወይም ማብራርያ እንድንሰጥ ወደ ኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ጥያቄዎች እየቀረቡ ሲሆን ፌዴሬሽናችን የቡድኑ አባላት መጥፋት ያሳዘነው መሆኑን እየገለጸ ታዳጊ ቡድኖች በመሰል ውድድሮች ላይ በራሳቸው ጥረት በሚያገኙት እድል ወደ ውድድሩ የሚያመሩ እንጂ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድንን የወከሉ አለመሆኑን እየገለፅን በአንዳድ አካላት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን አባላት እንደሆኑ እየተገለጸበት ያለው መንገድ ትክክል አለመሆኑን እናሳውቃለን። " ብሏል።
ከ77 ሀገራት የተውጣጡ ቡድኖች በተሳተፉበት በዚህ ውድድር ኢትዮጵያ በአራት ቡድኖች ተወክላ ነበር። ሆኖም የፍጻሜው ውድድር በሚካሄድበት ዕለት የተጫዋቾቹ ማረፊያ የነበረው ትምህርት ቤት አስተናጋጆች፣ አባላቱ እቃቸውን ጠቅልለው መጥፋታቸውን ደርሰውበታል። የጎቲያ ካፕ የፕሬስ ቃል አቀባይ ፍሬድሪክ ቤክማን፣ አዘጋጁ ኮሚቴ ከቡድኑ ጋር ጥሩ ግንኙነት ስለነበረው ድርጊቱ እንዳስገረማቸው ገልጸው፣ ለጥንቃቄ ሲባል ለፖሊስ ሪፖርት ማድረጋቸውን ተናግረዋል። ውድድሩ ከተጠናቀቀ አስር ቀናት ቢያልፉም፣ የቡድኑ አባላት እስካሁን ወደ ኢትዮጵያ አልተመለሱም።
አዘጋጆቹ ከቡድኑ አስተባባሪ በደረሳቸው የኢሜል መልእክት "የተፈጠረው የመግባባት ችግር ነው" የሚል ማስተባበያ ቢሰጥም፣ ተጫዋቾቹ የት እንዳሉ ግን ምንም ዓይነት ፍንጭ አልተሰጠም። የስዊድን ፖሊስ የጠፉ ሰዎችን የመፈለግ ክፍል ኃላፊ ኤሊኖር ሃልዲን እንደገለጹት፣ ከዚህ በፊት በውድድሩ ታሪክ ጥቂት ሰዎች የመጥፋት አጋጣሚ ቢኖርም፣ በአንድ ጊዜ 20 ሰዎች ሲሰወሩ ግን ይህ የመጀመሪያው ነው።
ፖሊስ ከስደተኞች ኤጀንሲ እና ከድንበር ተቆጣጣሪዎች ጋር በመተባበር ፍለጋውን የቀጠለ ሲሆን፣ ድርጊቱ በሰው አዘዋዋሪዎች የተፈጸመ ሳይሆን አባላቱ አስቀድመው ያቀዱት ስደት መሆኑን መረጃዎች ያመለክታሉ።
ይህ ክስተት ዓለም አቀፍ ስፖርታዊ መድረኮች ላልተገባ የስደት ዓላማ መጠቀሚያ እየሆኑ መምጣታቸውን የሚያሳይ አሳሳቢ አጋጣሚ ሆኗል። ታዳጊ አትሌቶች እና አጃቢዎቻቸው ሀገራቸውን ወክለው በሄዱበት የውድድር መድረክ ላይ መሰወራቸው፣ በሀገራት መካከል ያለውን እምነት ከመፈተኑም በላይ፤ በቀጣይ ሌሎች ወጣት ኢትዮጵያውያን ስፖርተኞች ዓለም አቀፍ የውድድር ዕድሎችን እንዳያገኙ እና የቪዛ ክልከላ እንዲያጋጥማቸው ሊያደርግ የሚችል አደገኛ አዝማሚያ መሆኑ የጉዳዩን አሳሳቢነት ያጎላዋል።
የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ባወጣው መግለጫ፤ "ዓመታዊው የጎቲያ ካፕ ውድድር ላይ ለመካፈል ወደ ስዊድን ያመሩ ታዳጊዎች እና የቡድን አባላት በስዊድን መጥፋታቸውን አስመልክቶ የተለያዩ መረጃዎች እየወጡ ይገኛሉ። በጉዳዩ ዙርያ ምላሽ ወይም ማብራርያ እንድንሰጥ ወደ ኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ጥያቄዎች እየቀረቡ ሲሆን ፌዴሬሽናችን የቡድኑ አባላት መጥፋት ያሳዘነው መሆኑን እየገለጸ ታዳጊ ቡድኖች በመሰል ውድድሮች ላይ በራሳቸው ጥረት በሚያገኙት እድል ወደ ውድድሩ የሚያመሩ እንጂ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድንን የወከሉ አለመሆኑን እየገለፅን በአንዳድ አካላት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን አባላት እንደሆኑ እየተገለጸበት ያለው መንገድ ትክክል አለመሆኑን እናሳውቃለን። " ብሏል።
7 days ago
የኢትዮጵያ አየር መንገድ የሰራተኞቹን የቤት ችግር ለመፍታት በጀመረው ስራ በጥር ወር 2 ሺ 500 የሚሆኑ ቤቶች ግንባታ ይጠናቀቃል አለ
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈጻሚ መስፍን ጣሰው የ2018 በጀት ዓመት አፈጻጸምን በተመለከተ በሰጡት መግለጫ 9 አዳዲስ የጉዞ አውሮፕላኖች እና ስምንት ዲኤ 40 ኤንጂ የተሰኙ ለፓይለቶች ማሰልጠኛ የሚሆኑ 8 አውሮፕላኖች መገዛታቸውን ገልጸዋል፡፡
በተጨማሪም በበጀት ዓመቱ በኢትዮጵያ የተለያዩ አካባቢዎች የሚገኙ ተርሚናሎችን የማደስና እንደ አዲስ የመስራት ተግባራት ተከናውነዋል ነው ያሉት፡፡የሰራተኞችን የቤት ችግር ለማቃለል በተጀመረው ስራ 5 ሺህ ለሚሆኑ ሰራተኞች የቤት ግንባታ መጀመሩን ጠቁመው፤ 2 ሺህ 500 የሚሆኑት ቤቶች እስከ 2019 ዓ.ም ጥር ወር ድረስ እንደሚጠናቀቁ አብራርተዋል፡፡
ቀሪዎቹ ቤቶች ደግሞ በ2019 ዓ.ም መጨረሻ ላይ ይጠናቀቃሉ ነው ያሉት፡፡የአየር መንገዱ የአቪየሽን ዩኒቨርሲቲ ከተቀበላቸው 2 ሺህ 183 ተማሪዎች ውስጥ 1 ሺህ 713 ተማሪዎችን ማስመረቅ መቻሉን አስረድተዋል፡፡
በበጀት ዓመቱ አየር መንገዱ ለበጎ አድራጎት ስራዎች ከ5 ነጥብ 6 ሚሊየን ብር በላይ የገንዘብ ድጋፍ ማድረጉን ገልጸዋል፡፡
Seledadotio
Seledadotio
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈጻሚ መስፍን ጣሰው የ2018 በጀት ዓመት አፈጻጸምን በተመለከተ በሰጡት መግለጫ 9 አዳዲስ የጉዞ አውሮፕላኖች እና ስምንት ዲኤ 40 ኤንጂ የተሰኙ ለፓይለቶች ማሰልጠኛ የሚሆኑ 8 አውሮፕላኖች መገዛታቸውን ገልጸዋል፡፡
በተጨማሪም በበጀት ዓመቱ በኢትዮጵያ የተለያዩ አካባቢዎች የሚገኙ ተርሚናሎችን የማደስና እንደ አዲስ የመስራት ተግባራት ተከናውነዋል ነው ያሉት፡፡የሰራተኞችን የቤት ችግር ለማቃለል በተጀመረው ስራ 5 ሺህ ለሚሆኑ ሰራተኞች የቤት ግንባታ መጀመሩን ጠቁመው፤ 2 ሺህ 500 የሚሆኑት ቤቶች እስከ 2019 ዓ.ም ጥር ወር ድረስ እንደሚጠናቀቁ አብራርተዋል፡፡
ቀሪዎቹ ቤቶች ደግሞ በ2019 ዓ.ም መጨረሻ ላይ ይጠናቀቃሉ ነው ያሉት፡፡የአየር መንገዱ የአቪየሽን ዩኒቨርሲቲ ከተቀበላቸው 2 ሺህ 183 ተማሪዎች ውስጥ 1 ሺህ 713 ተማሪዎችን ማስመረቅ መቻሉን አስረድተዋል፡፡
በበጀት ዓመቱ አየር መንገዱ ለበጎ አድራጎት ስራዎች ከ5 ነጥብ 6 ሚሊየን ብር በላይ የገንዘብ ድጋፍ ማድረጉን ገልጸዋል፡፡
Seledadotio
Seledadotio
7 days ago
አምስት ቋንቋዎች የፌዴራል የሥራ ቋንቋ እንዲሆኑ ምክረ ሀሳብ ከተሳታፊዎች ቀረበ።
👉 የውጭ ቋንቋዎች "የፌዴራል የሥራ ቋንቋ" እንዲሆኑ ምክረ ሀሳብ ቀርቦ "የኛን ቋንቋዎች ያጠፋል" በሚል አከራካሪ ሆኗል።
በምክክር ጉባዔው በ10 እና 50 ሰዎች ደረጃ የተደራጁ ንዑሳን ቡድኖች የተነጋሩባቸው የአጀንዳ ምክረ ሀሳቦች 250 ሰዎችን ለሚይዘው "ስልታዊ" ቡድን የመመራት ሂደት ላይ ደርሰዋል።
ጉባያተኞቹ ከሚመክሩባቸው 8 አጀንዳዎች መካከል "የሀገር ግንባታ" አንዱ ሲሆን፣ በዚሁ አጀንዳ ላይ በ10 እና 50 ሰዎች የተደራጁ ንዑሳን ቡድኖች በውይይታቸው ያቀረቧቸውን ዋና ዋና ምክረ ሀሳቦችን ጉዳዩን በጥልቅ የተከታተሉት የቲክቫህ ኢትዮጵያ ምንጭና ከሰላም ተፅዕኖ ፈጣሪ ኢትዮጵያውያን ማህበር የተወከሉት አቶ ከበደ ፉንዳ አብራርተዋል።
እኝሁ አካላት እንደገለጹት በዚሁ አጀንዳ፦
- ሀገር የማን ናት ? የብሔር ወይስ የዜጋ ?
- የኢትዮጵያ ማንነት ዜግነትን፣ ብሔርን፣ ወይስ መድብለ ብሔራዊ ፌዴራላዊ ማንትነን መሰረት ያደርግ፣
- ከ"እኛ" እና "እነርሱ" ከሚለው ከፋፋይ ትርክት እንዴት ወደ እኩልነትና የጋራ ተጠቃሚነት ስሜት እንደሚመጣ፣
- የሚጋጩ ታሪኮች እንዴት እንደሚታረቁ፣
- የጨቋኝ ተጨቋኝ ትርክት እንዴት እንደሚገመገም፣
- በኢትዮጵያ ባንዲራ ያለው አርማ እንዲወጣና በእርግብና በሌሎች ምልክቶች እንዲተካ፣
- በፌዴራል የሥራ ቋንቋ ጉዳይ እና በሌሎች ጉዳዮች የተለያዩ ምክረ ሀሳቦች ቀርበውበታል።
የፌዴራል የሥራ ቋንቋ ጉዳይ በሚመለከት ስለቀረቡ ምክረ ሀሳቦች ማብራሪያ የሰጡን ስማቸው እንዲጠቀስ ያልፈለጉ ታማኝ ምንጭ፣ " 'አማርኛ በብዙ ኢትዮጵያውያን የሚነገር ከመሆኑ አንፃር አሁን ያለው የፌዴራል የሥራ ቋንቋ መሆኑን ይዞ ይቀጥል፤ አማርኛ እና ኦሮምኛ የፌዴራል ቋንቋዎች ይሁኑ' " የሚሉ ምክረ ሀሳቦች መቅረባቸውን ተናግረዋል።
እንዲሁም ፦
° አማርኛ፣
° ኦሮምኛ፣
° ትግርኛ፣
° አፋርኛ፣
° ሶማሊኛ የፌዴራሉ የሥራ ቋንቋ ይሁኑ የሚሉ ሀሳቦች መቅረባቸውን ገልጸው፣ " 'አማርኛ ብሔራዊ ቋንቋ ሆኖ ሌሎቹ ደግሞ የፌዴራል የሥራ ቋንቋ ይሁኑ' የሚልም ሀሳብ አለ " ብለዋል።
• እንግሊዝኛ፣
• አረብኛ፣
• ፈረንሳይኛ፣
• ቻይንኛ የውጭ ሀገራት ቋንቋዎች "በትምህርት ሥርዓት ውስጥ እስከ ዩኒቨርሲቲ ድረስ" ቢካተቱ፣ "የፌዴራል የሥራ ቋንቋዎች ቢሆኑ" የሚሉ ሀሳቦች ቀርቦ፣ በሌላ በኩል ደግሞ "የኛን ቋንቋ ያጠፋል" በሚል አከራካሪ መሆኑን ጠቁመዋል።
ከሥራ እድል አኳያ እንዲሁም ኢትዮጵያ የአፍሪካ ህብረትና የሌሎች ዓለም አቀፍ ተቋማት መቀመጫ ከመሆኗ አንፃር፣ "ፈረንሳይኛ፣ ስዋህሊኛ፣ እንግሊዝኛ ቋንቋዎች በካሪኩለም ተካተው ኢትዮጵያውያን የሚማሩበት መሆን አለበት" የሚል ሀሳብ መቅረቡንም ምንጫችን ገልጸዋል።
የክልሎች የቋንቋ አጠቃቀምን በተመለከተ፥ የፌዴራል የሥራ ቋንቋ ሊሆኑ ይገባል ከሚባሉት መካከል ቢያንስ ሁለቱን ክልሎቹ ተጨማሪ የክልሉ የሥራ ቋንቋ አድርገው እንዲጠቀሙ ከተሳታፊዎች ምክረ ሀሳብ መሰንዘሩንም አስረድተዋል።
የፌዴራል የሥራ ቋንቋዎች መሆን ያለባቸው የሚመረጡት በክልሎቹ የህዝብ ቁጥር መሰረት እንዲሆን መጠየቁንም ያስረዱት ምንጫችን፣ የቀረቡት ምክረ ሀሳቦች ገና በቀጣዮቹ ቡድኖች ጭምር ምክክር እንደሚደረግባቸውና ገና ድምዳሜ ላይ እንዳልተደረሰባቸው አስገንዝበዋል።
የሀገር ግንባታን በተመለከተው አጀንዳ የተነሱ ሀሳቦች እየተደራጁ መሆኑን የነገሩን የሰላም ተፅዕኖ ፈጣሪ ኢትዮጵያውያን ማህበር ፕሬዚዳንት አቶ ከበደ ፉንዳ በበኩላቸው፣ የሥራ ቋንቋን በተመለከተ ከአማርኛ በተጨማሪ ያሉት ቋንቋዎችም እንዲመረጡ ምክረ ሀሳብ መቅረቡን ገልጸዋል።
የተነሱት ምክረ ሀሳቦች ገና በ250 እና 500 ቡድኖች እንዲሁም በ4,ዐዐ0 ተሳታፊዎች የሚመከርባቸው መሆናቸውን ተሳታፊዎቹ አስምረውበታል።
የኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር መስፍን ዓርዓያ፣ " ወገኖቻችን ቅርብ ለቅርብ ሆነው እየተከባበሩ እየተነጋገሩ ነው " ብለዋል።
"በሚቀጥለው ፌዝ መጋጨቶች ይጠበቃሉ። ምክንያቱም ሁላችንም ይዘን የመጣነውን ነው እዚህ የምናራግፈው። ስለዚህ ይሄ የመደማመጥ ፌዝ ነው" ያሉት መስፍን (ፕ/ር)፣ የመኳረፍና መከፋፈል ነገሮች ሊያጋጥሙ እንደሚችሉ ከዚህ ቀደም መናገራቸውን አስታውሰው፣ " ነገር ግን እንደተፈራው አይደለም " ብለዋል።
👉 የውጭ ቋንቋዎች "የፌዴራል የሥራ ቋንቋ" እንዲሆኑ ምክረ ሀሳብ ቀርቦ "የኛን ቋንቋዎች ያጠፋል" በሚል አከራካሪ ሆኗል።
በምክክር ጉባዔው በ10 እና 50 ሰዎች ደረጃ የተደራጁ ንዑሳን ቡድኖች የተነጋሩባቸው የአጀንዳ ምክረ ሀሳቦች 250 ሰዎችን ለሚይዘው "ስልታዊ" ቡድን የመመራት ሂደት ላይ ደርሰዋል።
ጉባያተኞቹ ከሚመክሩባቸው 8 አጀንዳዎች መካከል "የሀገር ግንባታ" አንዱ ሲሆን፣ በዚሁ አጀንዳ ላይ በ10 እና 50 ሰዎች የተደራጁ ንዑሳን ቡድኖች በውይይታቸው ያቀረቧቸውን ዋና ዋና ምክረ ሀሳቦችን ጉዳዩን በጥልቅ የተከታተሉት የቲክቫህ ኢትዮጵያ ምንጭና ከሰላም ተፅዕኖ ፈጣሪ ኢትዮጵያውያን ማህበር የተወከሉት አቶ ከበደ ፉንዳ አብራርተዋል።
እኝሁ አካላት እንደገለጹት በዚሁ አጀንዳ፦
- ሀገር የማን ናት ? የብሔር ወይስ የዜጋ ?
- የኢትዮጵያ ማንነት ዜግነትን፣ ብሔርን፣ ወይስ መድብለ ብሔራዊ ፌዴራላዊ ማንትነን መሰረት ያደርግ፣
- ከ"እኛ" እና "እነርሱ" ከሚለው ከፋፋይ ትርክት እንዴት ወደ እኩልነትና የጋራ ተጠቃሚነት ስሜት እንደሚመጣ፣
- የሚጋጩ ታሪኮች እንዴት እንደሚታረቁ፣
- የጨቋኝ ተጨቋኝ ትርክት እንዴት እንደሚገመገም፣
- በኢትዮጵያ ባንዲራ ያለው አርማ እንዲወጣና በእርግብና በሌሎች ምልክቶች እንዲተካ፣
- በፌዴራል የሥራ ቋንቋ ጉዳይ እና በሌሎች ጉዳዮች የተለያዩ ምክረ ሀሳቦች ቀርበውበታል።
የፌዴራል የሥራ ቋንቋ ጉዳይ በሚመለከት ስለቀረቡ ምክረ ሀሳቦች ማብራሪያ የሰጡን ስማቸው እንዲጠቀስ ያልፈለጉ ታማኝ ምንጭ፣ " 'አማርኛ በብዙ ኢትዮጵያውያን የሚነገር ከመሆኑ አንፃር አሁን ያለው የፌዴራል የሥራ ቋንቋ መሆኑን ይዞ ይቀጥል፤ አማርኛ እና ኦሮምኛ የፌዴራል ቋንቋዎች ይሁኑ' " የሚሉ ምክረ ሀሳቦች መቅረባቸውን ተናግረዋል።
እንዲሁም ፦
° አማርኛ፣
° ኦሮምኛ፣
° ትግርኛ፣
° አፋርኛ፣
° ሶማሊኛ የፌዴራሉ የሥራ ቋንቋ ይሁኑ የሚሉ ሀሳቦች መቅረባቸውን ገልጸው፣ " 'አማርኛ ብሔራዊ ቋንቋ ሆኖ ሌሎቹ ደግሞ የፌዴራል የሥራ ቋንቋ ይሁኑ' የሚልም ሀሳብ አለ " ብለዋል።
• እንግሊዝኛ፣
• አረብኛ፣
• ፈረንሳይኛ፣
• ቻይንኛ የውጭ ሀገራት ቋንቋዎች "በትምህርት ሥርዓት ውስጥ እስከ ዩኒቨርሲቲ ድረስ" ቢካተቱ፣ "የፌዴራል የሥራ ቋንቋዎች ቢሆኑ" የሚሉ ሀሳቦች ቀርቦ፣ በሌላ በኩል ደግሞ "የኛን ቋንቋ ያጠፋል" በሚል አከራካሪ መሆኑን ጠቁመዋል።
ከሥራ እድል አኳያ እንዲሁም ኢትዮጵያ የአፍሪካ ህብረትና የሌሎች ዓለም አቀፍ ተቋማት መቀመጫ ከመሆኗ አንፃር፣ "ፈረንሳይኛ፣ ስዋህሊኛ፣ እንግሊዝኛ ቋንቋዎች በካሪኩለም ተካተው ኢትዮጵያውያን የሚማሩበት መሆን አለበት" የሚል ሀሳብ መቅረቡንም ምንጫችን ገልጸዋል።
የክልሎች የቋንቋ አጠቃቀምን በተመለከተ፥ የፌዴራል የሥራ ቋንቋ ሊሆኑ ይገባል ከሚባሉት መካከል ቢያንስ ሁለቱን ክልሎቹ ተጨማሪ የክልሉ የሥራ ቋንቋ አድርገው እንዲጠቀሙ ከተሳታፊዎች ምክረ ሀሳብ መሰንዘሩንም አስረድተዋል።
የፌዴራል የሥራ ቋንቋዎች መሆን ያለባቸው የሚመረጡት በክልሎቹ የህዝብ ቁጥር መሰረት እንዲሆን መጠየቁንም ያስረዱት ምንጫችን፣ የቀረቡት ምክረ ሀሳቦች ገና በቀጣዮቹ ቡድኖች ጭምር ምክክር እንደሚደረግባቸውና ገና ድምዳሜ ላይ እንዳልተደረሰባቸው አስገንዝበዋል።
የሀገር ግንባታን በተመለከተው አጀንዳ የተነሱ ሀሳቦች እየተደራጁ መሆኑን የነገሩን የሰላም ተፅዕኖ ፈጣሪ ኢትዮጵያውያን ማህበር ፕሬዚዳንት አቶ ከበደ ፉንዳ በበኩላቸው፣ የሥራ ቋንቋን በተመለከተ ከአማርኛ በተጨማሪ ያሉት ቋንቋዎችም እንዲመረጡ ምክረ ሀሳብ መቅረቡን ገልጸዋል።
የተነሱት ምክረ ሀሳቦች ገና በ250 እና 500 ቡድኖች እንዲሁም በ4,ዐዐ0 ተሳታፊዎች የሚመከርባቸው መሆናቸውን ተሳታፊዎቹ አስምረውበታል።
የኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር መስፍን ዓርዓያ፣ " ወገኖቻችን ቅርብ ለቅርብ ሆነው እየተከባበሩ እየተነጋገሩ ነው " ብለዋል።
"በሚቀጥለው ፌዝ መጋጨቶች ይጠበቃሉ። ምክንያቱም ሁላችንም ይዘን የመጣነውን ነው እዚህ የምናራግፈው። ስለዚህ ይሄ የመደማመጥ ፌዝ ነው" ያሉት መስፍን (ፕ/ር)፣ የመኳረፍና መከፋፈል ነገሮች ሊያጋጥሙ እንደሚችሉ ከዚህ ቀደም መናገራቸውን አስታውሰው፣ " ነገር ግን እንደተፈራው አይደለም " ብለዋል።
7 days ago
የኢትዮጵያ አየር መንገድ 1.4 ትሪልየን ብር ገቢ ማግኘቱን አስታወቀ
**
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዛሬ ሐምሌ 22 ቀን 2018 ዓ.ም በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ፤ በበጀት ዓመቱ 1.4 ትሪልየን ብር ገቢ ማግኘቱን አስታውቋል።
የአየር መንገዱ ዋና ስራ አስፈፃሚ መስፍን ጣሰው እንደገለፁት፤ በአመቱ ከ20.1 ሚልየን በላይ መንገደኞችን እና 297 ሺህ ቶን የካርጎ ጭነቶችን ማጓጓዝ ተችሏል።
ከዚህ በተጨማሪም አየር መንገዱ የተለያዩ የአውሮፕላን ክፍሎችን የሚያመርት ሲሆን በዘንድሮው በጀት አመትም ለ68 አውሮፕላኖች የሚበቃ መለዋወጫ በማምረት ለቦይንግ ማቅረቡን ገልፀዋል።
በዚህም 6.2 ሚልየን ዶላር ገቢ ማግኘት እንደቻለ አስታውቀዋል።
Seledadotio
Seledadotio
**
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዛሬ ሐምሌ 22 ቀን 2018 ዓ.ም በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ፤ በበጀት ዓመቱ 1.4 ትሪልየን ብር ገቢ ማግኘቱን አስታውቋል።
የአየር መንገዱ ዋና ስራ አስፈፃሚ መስፍን ጣሰው እንደገለፁት፤ በአመቱ ከ20.1 ሚልየን በላይ መንገደኞችን እና 297 ሺህ ቶን የካርጎ ጭነቶችን ማጓጓዝ ተችሏል።
ከዚህ በተጨማሪም አየር መንገዱ የተለያዩ የአውሮፕላን ክፍሎችን የሚያመርት ሲሆን በዘንድሮው በጀት አመትም ለ68 አውሮፕላኖች የሚበቃ መለዋወጫ በማምረት ለቦይንግ ማቅረቡን ገልፀዋል።
በዚህም 6.2 ሚልየን ዶላር ገቢ ማግኘት እንደቻለ አስታውቀዋል።
Seledadotio
Seledadotio
7 days ago
የዘመን አቆጣጠራችን ይቀየር ተባለ‼️
በምክክሩ ላይ የኢትዮጵያን የዘመን አቆጣጠር በተመለከተ የተለያዩ አማራጮች ቀርበዋል።
በኢትዮጵያ የዘመን አቆጣጠር ውስጥ የሂጅራ ወይም የእስላማዊ የዘመን አቆጣጠር ይካተት፣ «ዓመተ ምህረት» የሚለው ይቅርና አሁን ያለው የፈረንጆቹ አቆጣጠር ይቀጥል፣ እንዲሁም ከእስልምናም ሆነ ከክርስትና ሃይማኖቶች ነፃ የሆነ የዘመን አቆጣጠር እንከተል የሚሉ ምክረ ሃሳቦች መቀረባቸው ታውቋል።
በተነሱት አጀንዳዎች ላይ እስካሁን ውሳኔ ደረጃ ላይ አልተደረሰም፣የውሳኔ ሂደቱ ገና መሆኑን ገልፀዋል።
Seledadotio
Seledadotio
በምክክሩ ላይ የኢትዮጵያን የዘመን አቆጣጠር በተመለከተ የተለያዩ አማራጮች ቀርበዋል።
በኢትዮጵያ የዘመን አቆጣጠር ውስጥ የሂጅራ ወይም የእስላማዊ የዘመን አቆጣጠር ይካተት፣ «ዓመተ ምህረት» የሚለው ይቅርና አሁን ያለው የፈረንጆቹ አቆጣጠር ይቀጥል፣ እንዲሁም ከእስልምናም ሆነ ከክርስትና ሃይማኖቶች ነፃ የሆነ የዘመን አቆጣጠር እንከተል የሚሉ ምክረ ሃሳቦች መቀረባቸው ታውቋል።
በተነሱት አጀንዳዎች ላይ እስካሁን ውሳኔ ደረጃ ላይ አልተደረሰም፣የውሳኔ ሂደቱ ገና መሆኑን ገልፀዋል።
Seledadotio
Seledadotio
Sponsored by
Surafel
7 days ago
የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ግንባታ ተጨባጭ ጉዞ
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 21፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በዓለም ላይ እያጋጠመ ያለውን የአየር ንብረት ለውጥ ፈተና ለመሻገር እየተወሰዱ ካሉ ርምጃዎች መካከል አረንጓዴ ኢኮኖሚ መገንባት አንደኛውና ዋነኛው ነው።
ኢትዮጵያ ከአረንጓዴ ኢኮኖሚ ግንባታ መሰረቶች ውስጥ ቀዳሚው የሆነውን የታዳሽ ኃይል ልማት በልዩ ትኩረት እየሰራች ትገኛለች።
የመደመር መንግሥት ሀገሪቱ በታዳሽ የሀይል ምንጮች ያላትን እምቅ አቅም በመጠቀም የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ሽግግርን እውን ለማድረግ በሰራው ስራ ተጨባጭ ውጤት አስመዝግቧል።
በውሃ፣ በፀሐይ፣ በንፋስ እና በጂኦተርማል ሀብቶች የታደለችው ኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦቷን በማዘመን የዜጎችን ኑሮ ከማሻሻል ባለፈ ለቀጣናዊ ትስስር ቁልፍ ሚና እየተጫወተች ትገኛለች።
ሀገሪቱ በአሁኑ ወቅት የምስራቅ አፍሪካ የሀይል ማዕከል ለመሆን በምታደርገው ጥረት የኤሌክትሪክ ሀይል መሰረተ ልማት ዝርጋታ የሀገሪቱን የሁለገብ ዕድገት ለማፋጠን ወሳኝ ሚና ይጫወታል።
የሀይል አቅርቦትን አስተማማኝና ተደራሽ ማድረግ የኢትዮጵያን የኢንዱስትሪ ፓርኮችና የግብርና ተቋማት ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚደረገው ጥረት አንኳር ጉዳይ ነው።
የሀገሪቱ የሀይል ምንጭ በዋናነት በውሃ ላይ የተመሰረተ ቢሆንም፤ በፀሐይና በንፋስ ሀይል እንዲታገዝ የሚደረገው ጥረት የላቀ ውጤት እያመጣ ይገኛል።
ለኢትዮጵያ አረንጓዴ ኢኮኖሚ ግንባታ የሀይል ዘርፉ ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከተ ሲሆን፥ በዘርፉ የተመዘገቡ ስኬቶችን አጠናክሮ ለማስቀጠል የሚያስችል ትኩረት ተሰጥቷል።
የአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫን ጨምሮ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ለአገልግሎት መብቃት የዘርፉን ተስፋ የሚጨበጥ አድርገውታል።
በግንባታ ላይ የሚገኘው የኮይሻ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ኢትዮጵያ በሀይል ልማት ቀጣናዊ ትስስርን ለመፍጠር የጀመረችውን ጉዞ ከዳር የማድረስ ቁመና ላይ መገኘቷን ያሳያል።
የሀገሪቱን ኢኮኖሚ እድገት መደገፍና የዜጎችን የኤሌክትሪክ ሀይል ፍላጎት የተሟላ ለማድረግ የሚሰራው የኤሌክትሪክ ሀይል የማመንጨት አቅም ተሻሽሏል።
ከንፋስ ኃይል፣ ከፀሐይ እና ከጂኦተርማል የሚመነጨው የኤሌክትሪክ ሀይል መጠን በከፍተኛ ፍጥነት እያደገ ይገኛል።
የኤሌክትሪክ ሀይል ከማመንጨት ስራው ጎን ለጎንም የሀይል ማመንጫ ጣቢያዎች ዝግጁነትን የማሳደግ ተግባር መከናወኑ አስተማማኝ የሀይል አቅርቦት አቅም እየተገነባ እንደሆነ ያመላክታል።
በአጠቃላይ የኤሌክትሪክ ሀይል በማመንጨት ዜጎችን ተጠቃሚ የማድረግና ቀጣናዊ ትስስርን የማጎልበት እንቅስቃሴ ባለፉት ዓመታት ተጨባጭ ውጤት አምጥቷል።
የዘርፉን አቅም በማጎልበት የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ግንባታ፣ የከተማና ገጠር ኤሌክትሪፊኬሽን እንዲሁም በኢነርጂ የቀጣናውን ሀገራት ይበልጥ ለማስተሳሰር የተጀመረው ጥረት ተጠናክሮ ቀጥሏል።
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 21፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በዓለም ላይ እያጋጠመ ያለውን የአየር ንብረት ለውጥ ፈተና ለመሻገር እየተወሰዱ ካሉ ርምጃዎች መካከል አረንጓዴ ኢኮኖሚ መገንባት አንደኛውና ዋነኛው ነው።
ኢትዮጵያ ከአረንጓዴ ኢኮኖሚ ግንባታ መሰረቶች ውስጥ ቀዳሚው የሆነውን የታዳሽ ኃይል ልማት በልዩ ትኩረት እየሰራች ትገኛለች።
የመደመር መንግሥት ሀገሪቱ በታዳሽ የሀይል ምንጮች ያላትን እምቅ አቅም በመጠቀም የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ሽግግርን እውን ለማድረግ በሰራው ስራ ተጨባጭ ውጤት አስመዝግቧል።
በውሃ፣ በፀሐይ፣ በንፋስ እና በጂኦተርማል ሀብቶች የታደለችው ኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦቷን በማዘመን የዜጎችን ኑሮ ከማሻሻል ባለፈ ለቀጣናዊ ትስስር ቁልፍ ሚና እየተጫወተች ትገኛለች።
ሀገሪቱ በአሁኑ ወቅት የምስራቅ አፍሪካ የሀይል ማዕከል ለመሆን በምታደርገው ጥረት የኤሌክትሪክ ሀይል መሰረተ ልማት ዝርጋታ የሀገሪቱን የሁለገብ ዕድገት ለማፋጠን ወሳኝ ሚና ይጫወታል።
የሀይል አቅርቦትን አስተማማኝና ተደራሽ ማድረግ የኢትዮጵያን የኢንዱስትሪ ፓርኮችና የግብርና ተቋማት ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚደረገው ጥረት አንኳር ጉዳይ ነው።
የሀገሪቱ የሀይል ምንጭ በዋናነት በውሃ ላይ የተመሰረተ ቢሆንም፤ በፀሐይና በንፋስ ሀይል እንዲታገዝ የሚደረገው ጥረት የላቀ ውጤት እያመጣ ይገኛል።
ለኢትዮጵያ አረንጓዴ ኢኮኖሚ ግንባታ የሀይል ዘርፉ ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከተ ሲሆን፥ በዘርፉ የተመዘገቡ ስኬቶችን አጠናክሮ ለማስቀጠል የሚያስችል ትኩረት ተሰጥቷል።
የአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫን ጨምሮ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ለአገልግሎት መብቃት የዘርፉን ተስፋ የሚጨበጥ አድርገውታል።
በግንባታ ላይ የሚገኘው የኮይሻ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ኢትዮጵያ በሀይል ልማት ቀጣናዊ ትስስርን ለመፍጠር የጀመረችውን ጉዞ ከዳር የማድረስ ቁመና ላይ መገኘቷን ያሳያል።
የሀገሪቱን ኢኮኖሚ እድገት መደገፍና የዜጎችን የኤሌክትሪክ ሀይል ፍላጎት የተሟላ ለማድረግ የሚሰራው የኤሌክትሪክ ሀይል የማመንጨት አቅም ተሻሽሏል።
ከንፋስ ኃይል፣ ከፀሐይ እና ከጂኦተርማል የሚመነጨው የኤሌክትሪክ ሀይል መጠን በከፍተኛ ፍጥነት እያደገ ይገኛል።
የኤሌክትሪክ ሀይል ከማመንጨት ስራው ጎን ለጎንም የሀይል ማመንጫ ጣቢያዎች ዝግጁነትን የማሳደግ ተግባር መከናወኑ አስተማማኝ የሀይል አቅርቦት አቅም እየተገነባ እንደሆነ ያመላክታል።
በአጠቃላይ የኤሌክትሪክ ሀይል በማመንጨት ዜጎችን ተጠቃሚ የማድረግና ቀጣናዊ ትስስርን የማጎልበት እንቅስቃሴ ባለፉት ዓመታት ተጨባጭ ውጤት አምጥቷል።
የዘርፉን አቅም በማጎልበት የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ግንባታ፣ የከተማና ገጠር ኤሌክትሪፊኬሽን እንዲሁም በኢነርጂ የቀጣናውን ሀገራት ይበልጥ ለማስተሳሰር የተጀመረው ጥረት ተጠናክሮ ቀጥሏል።
7 days ago
የኢትዮጵያውያን የጋራ ጉዳይ የባህር በር
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 21፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በድሮ ጊዜ ነገስታት የተለያዩ ሰዎችን ወደ ማህበረሰቡ እየላኩ "ሕዝቡ ምን አለ" በማለት ይጠይቁ እንደነበር ይነገራል፡፡
ይህ ዛሬም አለ፤ የኢትዮጵያ ሕዝብ የተሻለ ህይወት እንደሚገባው የሚያምነው ይህ መንግሥት ሕዝቡ ምን ይላል ሲል ይጠይቃል፤ የሕዝብን ጥያቄ ለመመለስም ይሰራል፡፡
ሕዝቡ ወጣት ልጆቹ ለስደትና እንግልት እንዳይዳረጉ፤ ይልቁንም በሀገራቸው ላይ የስራ እድልና በቂ ገቢ ማግኘት እንዳለባቸው ያምናል፡፡
ኢትዮጵያ እንድታድግና በቀደመው የሚያኮራ ማንነቷ እንድትታወቅ፤ እንደቀድሞው ሁሉ ለሌሎች ተምሳሌትነቷ እንዲቀጥል የሕዝብ ፍላጎት ነው፡፡
ሕዝብ ከዓለም ወደ ኋለ መቅረት ምርጫው አይደለም፤ የኢንተርኔት አገልግሎትን በበቂ ሁኔታ መጠቀም እንዲችል ዘመናዊና የሰለጠነ የአኗኗር ዘይቤ እንዲኖረው ይሻል፡፡
የኢትዮጵያ ሕዝብ ለልጆቹ ድህነትን ማውረስ አይፈልግም፤ አንዳንድ ሀገራት እንደሚያደርጉት ዛሬ የተገባን ኑሮ ከመኖር አልፎ ለነገ ትውልድ የሚተርፍ ሀብት ማስቀመጥ ምርጫው ነው፡፡
ኢትዮጵያ በምግብ ራስን ከመቻል አልፎ ቀጥተኛ የንግድ ግንኙነት ኖሯት ለሌሎች ሀገራት የሚሆኑ ምርቶችን መላክ እንድትችል፣ የውጪ ንግዷ አድጎ ጠንካራ የኢኮኖሚ አቅም እንዲኖረን የሕዝባችን ጽኑ ፍላጎት ነው፡፡
ኢትዮጵያ ሉዓላዊነቷ ተጠብቆ ተጽእኖ ፈጣሪነቷ እንዲጨምርና የዲፕሎማሲ አቅሟ እንዲያድግ እንዲሁም በራሷ ጉዳይ ላይ የሌሎች ጣልቃ ገብነት የሌለበት ውሳኔ ሰጪነት አቅም እንዲኖራት ይፈልጋል፡፡
ጠንካራ መሰረት ያላት የደህንነት አቅሟን የገነባች ሀገር ይፈልጋል፡፡
ከምንም በላይ ግን የኢትዮጵያ ህዝብ ያለአግባብ ለተፈጸመበት ታሪካዊ በደል የማይጓደል ፍትህን ይሻል፡፡
ይህን ጥያቄውን ሊያስመልስለት የሚችለውን ያለግባብ በሆነና ህጋዊ መሰረት በሌለው መንገድ የተነጠቀውን፣ በታሪክና ህግ የሚደገፈውን የባሕር በር የባለቤትነት መብቱን ከማስመለስ ወደ ኋላ አይልም፡፡
ኢትዮጵያ ዛሬ እየጠየቀች ያለችውን የባህር በር ጥያቄ መመለስ የኢትዮጵያውያንን የታሪክ፣ የፖለቲካና የኢኮኖሚ ጥያቄ ከመፍታት ባሻገር የህዝብ ስነ ልቦናን ለመጠበቅ ሚናው ትልቅ ነው፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እንዳሉት "የባሕር በር አልባነት፤ ገመና አልባነት ነው፡፡"
የኢትዮጵያ ሕዝብ ችግሩን ከመደበቅ ልምምድ ወጥቶ መፍትሄ ለመስጠት በሚሄድባቸው መንገዶች ሁሉ የባሕር በር የሁሉንም ኢትዮጵያዊ ጥያቄ ለመመለስ የሚያስችል አማራጭ አልባ መፍትሄ ነው፡፡
በቤተልሔም ግርማ
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 21፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በድሮ ጊዜ ነገስታት የተለያዩ ሰዎችን ወደ ማህበረሰቡ እየላኩ "ሕዝቡ ምን አለ" በማለት ይጠይቁ እንደነበር ይነገራል፡፡
ይህ ዛሬም አለ፤ የኢትዮጵያ ሕዝብ የተሻለ ህይወት እንደሚገባው የሚያምነው ይህ መንግሥት ሕዝቡ ምን ይላል ሲል ይጠይቃል፤ የሕዝብን ጥያቄ ለመመለስም ይሰራል፡፡
ሕዝቡ ወጣት ልጆቹ ለስደትና እንግልት እንዳይዳረጉ፤ ይልቁንም በሀገራቸው ላይ የስራ እድልና በቂ ገቢ ማግኘት እንዳለባቸው ያምናል፡፡
ኢትዮጵያ እንድታድግና በቀደመው የሚያኮራ ማንነቷ እንድትታወቅ፤ እንደቀድሞው ሁሉ ለሌሎች ተምሳሌትነቷ እንዲቀጥል የሕዝብ ፍላጎት ነው፡፡
ሕዝብ ከዓለም ወደ ኋለ መቅረት ምርጫው አይደለም፤ የኢንተርኔት አገልግሎትን በበቂ ሁኔታ መጠቀም እንዲችል ዘመናዊና የሰለጠነ የአኗኗር ዘይቤ እንዲኖረው ይሻል፡፡
የኢትዮጵያ ሕዝብ ለልጆቹ ድህነትን ማውረስ አይፈልግም፤ አንዳንድ ሀገራት እንደሚያደርጉት ዛሬ የተገባን ኑሮ ከመኖር አልፎ ለነገ ትውልድ የሚተርፍ ሀብት ማስቀመጥ ምርጫው ነው፡፡
ኢትዮጵያ በምግብ ራስን ከመቻል አልፎ ቀጥተኛ የንግድ ግንኙነት ኖሯት ለሌሎች ሀገራት የሚሆኑ ምርቶችን መላክ እንድትችል፣ የውጪ ንግዷ አድጎ ጠንካራ የኢኮኖሚ አቅም እንዲኖረን የሕዝባችን ጽኑ ፍላጎት ነው፡፡
ኢትዮጵያ ሉዓላዊነቷ ተጠብቆ ተጽእኖ ፈጣሪነቷ እንዲጨምርና የዲፕሎማሲ አቅሟ እንዲያድግ እንዲሁም በራሷ ጉዳይ ላይ የሌሎች ጣልቃ ገብነት የሌለበት ውሳኔ ሰጪነት አቅም እንዲኖራት ይፈልጋል፡፡
ጠንካራ መሰረት ያላት የደህንነት አቅሟን የገነባች ሀገር ይፈልጋል፡፡
ከምንም በላይ ግን የኢትዮጵያ ህዝብ ያለአግባብ ለተፈጸመበት ታሪካዊ በደል የማይጓደል ፍትህን ይሻል፡፡
ይህን ጥያቄውን ሊያስመልስለት የሚችለውን ያለግባብ በሆነና ህጋዊ መሰረት በሌለው መንገድ የተነጠቀውን፣ በታሪክና ህግ የሚደገፈውን የባሕር በር የባለቤትነት መብቱን ከማስመለስ ወደ ኋላ አይልም፡፡
ኢትዮጵያ ዛሬ እየጠየቀች ያለችውን የባህር በር ጥያቄ መመለስ የኢትዮጵያውያንን የታሪክ፣ የፖለቲካና የኢኮኖሚ ጥያቄ ከመፍታት ባሻገር የህዝብ ስነ ልቦናን ለመጠበቅ ሚናው ትልቅ ነው፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እንዳሉት "የባሕር በር አልባነት፤ ገመና አልባነት ነው፡፡"
የኢትዮጵያ ሕዝብ ችግሩን ከመደበቅ ልምምድ ወጥቶ መፍትሄ ለመስጠት በሚሄድባቸው መንገዶች ሁሉ የባሕር በር የሁሉንም ኢትዮጵያዊ ጥያቄ ለመመለስ የሚያስችል አማራጭ አልባ መፍትሄ ነው፡፡
በቤተልሔም ግርማ
Comments