2 hours ago
ወደ ዘላቂ ልማት የሚደረግ ሽግግር
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 28፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ኢትዮጵያ ለመዋቅራዊ ሽግግር፣ ለኢኮኖሚ ጥንካሬ እና ለአካታች ሀገራዊ እድገት ቁርጠኝነት ባለው ሥርዓት እየተመራች በዘመናዊ ታሪክ ግንባታዋ ወሳኝ ምዕራፍ ላይ ትገኛለች።
በሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ ኢትዮጵያ በዋና ዋና ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ዘርፎች ላይ አበይት ስኬቶችን እያስመዘገበች ነው፡፡
የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ መሰረት የሆነው ግብርና ወደ ቴክኖሎጂ መር ያደረገው ሽግግር ተጨባጭ ውጤት እያስመዘገበ ይገኛል፡፡
በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት እና በክላስተር እርሻ እቅዶች አማካኝነት ኢትዮጵያ የሀገር ውስጥ ምርትን በከፍተኛ ሁኔታ አሳድጋለች፡፡ይህም ከውጭ የሚገቡ ምርቶች ጥገኝነትን ቀንሷል፡፡
በሀገሪቱ በአረንጓዴ ዐሻራ ፕሮግራሞች በአትክልትና ፍራፍሬ ላይ የተደረጉ ኢንቨስትመንቶች የአየር ንብረት ተፅዕኖን ለመቋቋም ሥነ ምህዳርን ለማከም እና የኑሮ ውድነትን ለማረጋጋት የሚደረገውን ጉዞ እየደገፈ ነው፡፡
የኃይል ማመንጨት አቅምን በማሳደግ የመንገድ መረቦችን በማዘመን እና በማስተሳሰር የኢትዮጵያ የመሰረተ ልማት ገጽታ አስደናቂ ለውጥ በማድረግ፤ የሀገር ውስጥ ትስስርን እያጠናከረ ኢትዮጵያን በአህጉራዊ ነጻ ንግድ ቀጣና ስር የንግድ ማዕከል እያደረጋት ይገኛል።
በአዲስ አበባ እና በክልል ከተሞች የተካሄደው የኮሪደር ልማት የሕዝብ ቦታዎችን በመሠረታዊነት በማደስ፤ መንገዶችን በማዘመን፣ አረንጓዴ የሕዝብ ቦታዎችን በመገንባት፣ የመገልገያ መሠረተ ልማቶችን በማስፋፋት እና የንፅህና አጠባበቅ ሥርዓቶችን በማሻሻል ተስማሚ የከተማ አካባቢን እየፈጠረ ነው፡፡
ዘላቂ ኢኮኖሚ ለመገንባት ኢትዮጵያ በዲጂታል ኢትዮጵያ ስትራቴጂ አማካኝነት የዲጂታል ሽግግርን በከፍተኛ ሁኔታ እያፋጠነች ትገኛለች።
በቴሌኮሙኒኬሽን እና በፋይናንስ ዘርፍ ላይ የተደረጉ ኢንቨስትመንቶች የፋይናንስ አካታችነትን እያሳደገ ነው፡፡
የኢንዱስትሪ ፓርኮችን ለማስፋፋት የሀገር ውስጥ ማኑፋክቸሪንግን ለማነቃቃት እና ከፍተኛ ዋጋ ያላቸውን የውጭ ኢንቨስትመንቶችን ለመሳብ የሚደረጉ ጥረቶች የኤክስፖርት ገቢን በማሳደግ የሰለጠነ የሰው ሀይል መፍጠራቸውን ቀጥለዋል።
የኢኮኖሚ እድገት ያለ ማህበራዊ ልማት ትርጉም የለውምና የኢትዮጵያ መንግሥት በትምህርት፣ ጤና እና ሌሎች ዘርፎች መሠረተ ልማቶችን በማሻሻል የሰራተኛውን ክህሎት ከዘመናዊ የገበያ ፍላጎት ጋር በማጣጣም የዜጎችን ሁለንተናዊ ለውጥ ማጠናከር ተችሏል።
ኢትዮጵያ እስካሁን ላስመዘገበቻቸው ስኬቶች በዓለም አቀፍ ደረጃ የተሰጧት እውቅናዎች የበለጸገች ሉዓላዊት ሀገር ለመገንባት በሚደረገው ጥረት ውስጥ ፈተናዎች ቢኖሩም ህዝብ ከውጤት ተኮር አመራር ጋር ተቀናጅቶ ወደ ዘላቂ ልማት የሚያደርገው ጉዞ በተገቢ መስመር ላይ ስለመሆኑ ማሳያ ናቸው።
በምሕረት ደምሴ
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 28፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ኢትዮጵያ ለመዋቅራዊ ሽግግር፣ ለኢኮኖሚ ጥንካሬ እና ለአካታች ሀገራዊ እድገት ቁርጠኝነት ባለው ሥርዓት እየተመራች በዘመናዊ ታሪክ ግንባታዋ ወሳኝ ምዕራፍ ላይ ትገኛለች።
በሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ ኢትዮጵያ በዋና ዋና ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ዘርፎች ላይ አበይት ስኬቶችን እያስመዘገበች ነው፡፡
የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ መሰረት የሆነው ግብርና ወደ ቴክኖሎጂ መር ያደረገው ሽግግር ተጨባጭ ውጤት እያስመዘገበ ይገኛል፡፡
በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት እና በክላስተር እርሻ እቅዶች አማካኝነት ኢትዮጵያ የሀገር ውስጥ ምርትን በከፍተኛ ሁኔታ አሳድጋለች፡፡ይህም ከውጭ የሚገቡ ምርቶች ጥገኝነትን ቀንሷል፡፡
በሀገሪቱ በአረንጓዴ ዐሻራ ፕሮግራሞች በአትክልትና ፍራፍሬ ላይ የተደረጉ ኢንቨስትመንቶች የአየር ንብረት ተፅዕኖን ለመቋቋም ሥነ ምህዳርን ለማከም እና የኑሮ ውድነትን ለማረጋጋት የሚደረገውን ጉዞ እየደገፈ ነው፡፡
የኃይል ማመንጨት አቅምን በማሳደግ የመንገድ መረቦችን በማዘመን እና በማስተሳሰር የኢትዮጵያ የመሰረተ ልማት ገጽታ አስደናቂ ለውጥ በማድረግ፤ የሀገር ውስጥ ትስስርን እያጠናከረ ኢትዮጵያን በአህጉራዊ ነጻ ንግድ ቀጣና ስር የንግድ ማዕከል እያደረጋት ይገኛል።
በአዲስ አበባ እና በክልል ከተሞች የተካሄደው የኮሪደር ልማት የሕዝብ ቦታዎችን በመሠረታዊነት በማደስ፤ መንገዶችን በማዘመን፣ አረንጓዴ የሕዝብ ቦታዎችን በመገንባት፣ የመገልገያ መሠረተ ልማቶችን በማስፋፋት እና የንፅህና አጠባበቅ ሥርዓቶችን በማሻሻል ተስማሚ የከተማ አካባቢን እየፈጠረ ነው፡፡
ዘላቂ ኢኮኖሚ ለመገንባት ኢትዮጵያ በዲጂታል ኢትዮጵያ ስትራቴጂ አማካኝነት የዲጂታል ሽግግርን በከፍተኛ ሁኔታ እያፋጠነች ትገኛለች።
በቴሌኮሙኒኬሽን እና በፋይናንስ ዘርፍ ላይ የተደረጉ ኢንቨስትመንቶች የፋይናንስ አካታችነትን እያሳደገ ነው፡፡
የኢንዱስትሪ ፓርኮችን ለማስፋፋት የሀገር ውስጥ ማኑፋክቸሪንግን ለማነቃቃት እና ከፍተኛ ዋጋ ያላቸውን የውጭ ኢንቨስትመንቶችን ለመሳብ የሚደረጉ ጥረቶች የኤክስፖርት ገቢን በማሳደግ የሰለጠነ የሰው ሀይል መፍጠራቸውን ቀጥለዋል።
የኢኮኖሚ እድገት ያለ ማህበራዊ ልማት ትርጉም የለውምና የኢትዮጵያ መንግሥት በትምህርት፣ ጤና እና ሌሎች ዘርፎች መሠረተ ልማቶችን በማሻሻል የሰራተኛውን ክህሎት ከዘመናዊ የገበያ ፍላጎት ጋር በማጣጣም የዜጎችን ሁለንተናዊ ለውጥ ማጠናከር ተችሏል።
ኢትዮጵያ እስካሁን ላስመዘገበቻቸው ስኬቶች በዓለም አቀፍ ደረጃ የተሰጧት እውቅናዎች የበለጸገች ሉዓላዊት ሀገር ለመገንባት በሚደረገው ጥረት ውስጥ ፈተናዎች ቢኖሩም ህዝብ ከውጤት ተኮር አመራር ጋር ተቀናጅቶ ወደ ዘላቂ ልማት የሚያደርገው ጉዞ በተገቢ መስመር ላይ ስለመሆኑ ማሳያ ናቸው።
በምሕረት ደምሴ
5 hours ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የኢስቶኒያ ፖሊስ ኦገስት ሦስት ቀን በዋና ከተማዋ ታሊን ውስጥ፣ ሀገሪቱን በህገወጥ መንገድ አቋርጠው ገብተዋል በሚል ጥርጣሬ በሁለት ቡድን የተከፈሉ ስምንት ሰዎችን በቁጥጥር ስር አውሏል። የሰሜናዊ ፖሊስ እዝ የፕሬስ አገልግሎት እንዳስታወቀው፣ በመጀመሪያ በታሊን በሚገኘው ታምሳሬ ፓርክ ውስጥ ስድስት ሰዎች የተያዙ ሲሆን፣ ግለሰቦቹ ከኢትዮጵያ እንደመጡ እና ወደ አውሮፓ የገቡትም ቤላሩስን አቋርጠው መሆኑን ለፖሊስ ተናግረዋል።
በዚሁ ዕለት በከተማዋ መሀል ተጨማሪ ሁለት ግለሰቦች የተያዙ ሲሆን፣ እነዚህም በተመሳሳይ ከኢትዮጵያ እንደመጡ ተናግረዋል። ሁለቱ ግለሰቦች ምንም ዓይነት የማንነት መታወቂያ ሰነድ ያልነበራቸው ሲሆን፣ ከዚህ ቀደም ከተያዙት ስድስት ሰዎች ጋር በመሆን ሁሉም ለውጭ ዜጎች ወደተዘጋጀው ጊዜያዊ ማቆያ ማዕከል ተወስደዋል።
በኢስቶኒያ ባለፉት ጥቂት ሳምንታት ውስጥ በደርዘን የሚቆጠሩ ህገወጥ ስደተኞች በቁጥጥር ስር መዋላቸው ተዘግቧል። የሀገሪቱ ፖሊስ እንዳረጋገጠው፣ የተደራጁ ወንጀለኛ ቡድኖች ስደተኞቹን በኢስቶኒያ አቋርጠው ወደ ሌሎች ሀገራት ለማሻገር ሙከራ እያደረጉ ይገኛሉ።
በዚሁ ዕለት በከተማዋ መሀል ተጨማሪ ሁለት ግለሰቦች የተያዙ ሲሆን፣ እነዚህም በተመሳሳይ ከኢትዮጵያ እንደመጡ ተናግረዋል። ሁለቱ ግለሰቦች ምንም ዓይነት የማንነት መታወቂያ ሰነድ ያልነበራቸው ሲሆን፣ ከዚህ ቀደም ከተያዙት ስድስት ሰዎች ጋር በመሆን ሁሉም ለውጭ ዜጎች ወደተዘጋጀው ጊዜያዊ ማቆያ ማዕከል ተወስደዋል።
በኢስቶኒያ ባለፉት ጥቂት ሳምንታት ውስጥ በደርዘን የሚቆጠሩ ህገወጥ ስደተኞች በቁጥጥር ስር መዋላቸው ተዘግቧል። የሀገሪቱ ፖሊስ እንዳረጋገጠው፣ የተደራጁ ወንጀለኛ ቡድኖች ስደተኞቹን በኢስቶኒያ አቋርጠው ወደ ሌሎች ሀገራት ለማሻገር ሙከራ እያደረጉ ይገኛሉ።
6 hours ago
የ6ኛ ክፍል ሚኒስትሪ ፈተናን 81 ትምህርት ቤቶች አንድም ተማሪ አላሳለፉም ተባለ
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ትምህርት ቢሮ የ2018 ዓ.ም የ6ኛ እና የ8ኛ ክፍል ማለፊያ ነጥብ ክልላዊ ፈተና 50 እና ከዚያ በላይ መሆኑን ገልጿል።ድጋፍ ለሚያስፈልጋቸው ደግሞ 48 እና ከዛ በላይ ማለፊያ ነጥብ ተቆርጦለታል።የ8ኛ ክፍል ፈተናን ለመውሰድ የተመዘገቡ ተማሪዎች 86 ሺህ 502 እንደሆኑ የተገለፀ ሲሆን 78 ሺህ 203 የሚሆኑት ፈተናውን ወስደዋል።
ከእነዚህ ውስጥ ወደ ቀጣይ ክፍል ያለፋት 47 ሺህ 307 ተማሪዎች መሆናቸውን የጂንካ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች የህዝብና ሚዲያ ግንኙነት ዳይሬክተር አቶ የሱፍ አህመድ ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል።በዚህም መሠረት ክልላዊ ውጤት ከመቶ አንፃር ሲታይ 60 ነጥብ 4 መሆኑ ተገልጿል።በተመሳሳይ የ6ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ለመውሰድ የተመዘገቡ ተፈታኞች 126 ሺህ 224 ናቸው። ፈተና የወሰዱት ደግሞ 110 ሺህ 566 ከእነዚህ ደግሞ ማለፊያ ነጥብ አስመዝግበው ወደ ቀጣይ 7ኛ ክፍል የተዛወሩ 70 ሺህ 584 መሆናቸውን አቶ የሱፍ ነግረውናል።
በዚህም ክልላዊ ውጤት በመቶ ሲገለፅ 63 ነጥብ 8 እንደሆነ ተገልጿል። 540 ትምህርት ቤቶች የ8ኛ ክፍል ተማሪዎቻቸውን ሙሉ በሙሉ አሳልፈዋል።በተመሳሳይ የ6ኛ ክፍል ፈተናን አስመልክቶ 476 ትምህርት ቤቶች ሙሉ በሙሉ ተማሪዎቻቸውን ሲያሳልፉ 81 ትምህርት ቤቶች ደግሞ አንድም ተማሪ አላሳለፉም።
በአጠቃላይ ክልላዊ ውጤቱ ከአምና የትምህርት ዘመን ውጤት ጋር ሲነፃፀር የ8ኛ ክፍል በ3 በመቶ ያነሰ አፈፃፀምን አስመዝግቧል ። አምና በነበረው ክልላዊ ውጤት 63 በመቶ የሆነ ውጤት ተመዝግቦበት እንደነበር ተገልጿል።በተመሳሳይ የ6ኛ ክፍል የአምና ክልላዊ ውጤትን በተመለከተ 56 በመቶ አፈፃፀም የታየበት እንደነበር የተነገረ ሲሆን በ2018 በጀት አመት ደግሞ 63 ነጥብ 84 በመቶ መሆኑን አቶ የሱፍ አህመድ ጨምረው ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል።
Seledadotio
Seledadotio
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ትምህርት ቢሮ የ2018 ዓ.ም የ6ኛ እና የ8ኛ ክፍል ማለፊያ ነጥብ ክልላዊ ፈተና 50 እና ከዚያ በላይ መሆኑን ገልጿል።ድጋፍ ለሚያስፈልጋቸው ደግሞ 48 እና ከዛ በላይ ማለፊያ ነጥብ ተቆርጦለታል።የ8ኛ ክፍል ፈተናን ለመውሰድ የተመዘገቡ ተማሪዎች 86 ሺህ 502 እንደሆኑ የተገለፀ ሲሆን 78 ሺህ 203 የሚሆኑት ፈተናውን ወስደዋል።
ከእነዚህ ውስጥ ወደ ቀጣይ ክፍል ያለፋት 47 ሺህ 307 ተማሪዎች መሆናቸውን የጂንካ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች የህዝብና ሚዲያ ግንኙነት ዳይሬክተር አቶ የሱፍ አህመድ ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል።በዚህም መሠረት ክልላዊ ውጤት ከመቶ አንፃር ሲታይ 60 ነጥብ 4 መሆኑ ተገልጿል።በተመሳሳይ የ6ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ለመውሰድ የተመዘገቡ ተፈታኞች 126 ሺህ 224 ናቸው። ፈተና የወሰዱት ደግሞ 110 ሺህ 566 ከእነዚህ ደግሞ ማለፊያ ነጥብ አስመዝግበው ወደ ቀጣይ 7ኛ ክፍል የተዛወሩ 70 ሺህ 584 መሆናቸውን አቶ የሱፍ ነግረውናል።
በዚህም ክልላዊ ውጤት በመቶ ሲገለፅ 63 ነጥብ 8 እንደሆነ ተገልጿል። 540 ትምህርት ቤቶች የ8ኛ ክፍል ተማሪዎቻቸውን ሙሉ በሙሉ አሳልፈዋል።በተመሳሳይ የ6ኛ ክፍል ፈተናን አስመልክቶ 476 ትምህርት ቤቶች ሙሉ በሙሉ ተማሪዎቻቸውን ሲያሳልፉ 81 ትምህርት ቤቶች ደግሞ አንድም ተማሪ አላሳለፉም።
በአጠቃላይ ክልላዊ ውጤቱ ከአምና የትምህርት ዘመን ውጤት ጋር ሲነፃፀር የ8ኛ ክፍል በ3 በመቶ ያነሰ አፈፃፀምን አስመዝግቧል ። አምና በነበረው ክልላዊ ውጤት 63 በመቶ የሆነ ውጤት ተመዝግቦበት እንደነበር ተገልጿል።በተመሳሳይ የ6ኛ ክፍል የአምና ክልላዊ ውጤትን በተመለከተ 56 በመቶ አፈፃፀም የታየበት እንደነበር የተነገረ ሲሆን በ2018 በጀት አመት ደግሞ 63 ነጥብ 84 በመቶ መሆኑን አቶ የሱፍ አህመድ ጨምረው ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል።
Seledadotio
Seledadotio
7 hours ago
ጓቲማላ የፉዌጎ እሳተ ገሞራ ፈንድቶ ከፍተኛ የአደጋ ማንቂያ ታወጀ
#ethiopia | ጓቲማላ መንግሥት የመካከለኛው አሜሪካ እጅግ ንቁ ከሆኑ እሳተ ገሞራዎች አንዱ የሆነው ፉዌጎ (Fuego) ከባድ ፍንዳታ ካሳየ በኋላ በመላ ሀገሪቱ ሁለተኛውን ከፍተኛ የአደጋ ማንቂያ (Orange Alert) አውጇል።
ባለሥልጣናት ከእሳተ ገሞራው አቅራቢያ የሚገኙ ሁለት መንደሮችን በአስቸኳይ እንዲለቁ ትዕዛዝ ሰጥተዋል።
የላቫ ፍሰት፣ የአመድ ደመና እና ፓይሮክላስቲክ ፍሰቶች (በከፍተኛ ፍጥነት የሚንቀሳቀሱ የሞቃት ጋዝ፣ አመድ እና ድንጋይ ድብልቆች) በአካባቢው ላይ አደጋ ሊያስከትሉ ስለሚችሉ የመከላከያ እርምጃዎች ተጠናክረዋል።
በተጨማሪም በአካባቢው ያሉ ትምህርት ቤቶች ለጊዜው ተዘግተዋል፣ ወደ ታሪካዊቷ አንቲጓ ከተማ የሚያመራው ዋና መንገድም ተዘግቷል።
በአሁኑ ወቅት የሟቾች ወይም የከባድ ጉዳት ሪፖርት አልወጣም፣ ነገር ግን ባለሥልጣናት የእሳተ ገሞራውን እንቅስቃሴ በቅርብ እየተከታተሉ ነው።
ፉዌጎ እሳተ ገሞራ በ2018 በፈነዳበት ወቅት በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ሕይወታቸውን አጥተው ነበር፤ ስለዚህ የአሁኑ ፍንዳታ በባለሥልጣናት በከፍተኛ ጥንቃቄ እየተያዘ ነው።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#ethiopia | ጓቲማላ መንግሥት የመካከለኛው አሜሪካ እጅግ ንቁ ከሆኑ እሳተ ገሞራዎች አንዱ የሆነው ፉዌጎ (Fuego) ከባድ ፍንዳታ ካሳየ በኋላ በመላ ሀገሪቱ ሁለተኛውን ከፍተኛ የአደጋ ማንቂያ (Orange Alert) አውጇል።
ባለሥልጣናት ከእሳተ ገሞራው አቅራቢያ የሚገኙ ሁለት መንደሮችን በአስቸኳይ እንዲለቁ ትዕዛዝ ሰጥተዋል።
የላቫ ፍሰት፣ የአመድ ደመና እና ፓይሮክላስቲክ ፍሰቶች (በከፍተኛ ፍጥነት የሚንቀሳቀሱ የሞቃት ጋዝ፣ አመድ እና ድንጋይ ድብልቆች) በአካባቢው ላይ አደጋ ሊያስከትሉ ስለሚችሉ የመከላከያ እርምጃዎች ተጠናክረዋል።
በተጨማሪም በአካባቢው ያሉ ትምህርት ቤቶች ለጊዜው ተዘግተዋል፣ ወደ ታሪካዊቷ አንቲጓ ከተማ የሚያመራው ዋና መንገድም ተዘግቷል።
በአሁኑ ወቅት የሟቾች ወይም የከባድ ጉዳት ሪፖርት አልወጣም፣ ነገር ግን ባለሥልጣናት የእሳተ ገሞራውን እንቅስቃሴ በቅርብ እየተከታተሉ ነው።
ፉዌጎ እሳተ ገሞራ በ2018 በፈነዳበት ወቅት በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ሕይወታቸውን አጥተው ነበር፤ ስለዚህ የአሁኑ ፍንዳታ በባለሥልጣናት በከፍተኛ ጥንቃቄ እየተያዘ ነው።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
8 hours ago
ከሁለት ሚሊየን ብር በላይ የሚገመት የወንዶች አልባሳትን የሰረቁ 6 ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ዋሉ
የወንጀል ድርጊቱ የተፈፀመው ሐምሌ 21 ቀን 2018 ዓ/ም ከሌሊቱ 9 ሠዓት በልደታ ክ/ከተማ ወረዳ 1 መቻሬ ሜዳ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ነው።
ተጠርጣሪዎቹ ደብሩ መለሰ፣ ሞገስ ተካይ፣ ብርሃኑ አያሌው፣ ዘሪሁን በለጠ፣ ሚሊዮን መስፍን እና አብዱልሰላም ነስረዲን የተባሉ ሲሆኑ የሠሌዳ ቁጥር ኮድ 3 B 40762 አዲስ አበባ የሆነ ቪትስ ተሽከርካሪ በመጠቀም አንድ የወንዶች አልባሳት መሸጫ ሱቅ ገንጥለው ገብተዋል።
ግምታዊ ዋጋቸው ከሁለት ሚሊዮን ብር በላይ የሚያወጡ የወንዶች ሱሪ፣ ጫማ እና ቲሸርቶችን ሰርቀው ሊሰወሩ ሲሉ ድርጊቱን በተመለከቱ ግለሰቦች እና በፖሊስ አባላት በቁጥጥር ስር ውለዋል፡፡
ፖሊስ በወቅቱ ተጠርጣሪዎቹን በቁጥጥር ስር ባዋለበት ወቅት ባደረገው ፍተሻ ከሌሎች ክፍለ ከተሞች ከሰረቁት የጎማ ጎሚኒ እና የኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ ኬብል ጋር በቁጥጥር ስር ውለው ምርመራ እየተጣራባቸው እንደሚገኝ የልደታ ክ/ከተማ ፖሊስ ዋና መምሪያ ገልጾ ተገቢውን ማስረጃ በማጠናቀር ክስ እንደሚያስመሰርትም አስታውቋል፡፡
የክረምት ወቅት እንደመሆኑ መጠን ጨለማን እና ዝናብን እንደምቹ አጋጣሚ በመጠቀም የሚፈፀሙ ወንጀሎችን ለመከላከል የንግድ ተቋማትም ሆኑ ድርጅቶች የጥበቃ አቅማቸውን ማጠናከር እንደሚጠበቅባቸውም የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ አስታውቋል፡፡
Seledadotio
Seledadotio
የወንጀል ድርጊቱ የተፈፀመው ሐምሌ 21 ቀን 2018 ዓ/ም ከሌሊቱ 9 ሠዓት በልደታ ክ/ከተማ ወረዳ 1 መቻሬ ሜዳ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ነው።
ተጠርጣሪዎቹ ደብሩ መለሰ፣ ሞገስ ተካይ፣ ብርሃኑ አያሌው፣ ዘሪሁን በለጠ፣ ሚሊዮን መስፍን እና አብዱልሰላም ነስረዲን የተባሉ ሲሆኑ የሠሌዳ ቁጥር ኮድ 3 B 40762 አዲስ አበባ የሆነ ቪትስ ተሽከርካሪ በመጠቀም አንድ የወንዶች አልባሳት መሸጫ ሱቅ ገንጥለው ገብተዋል።
ግምታዊ ዋጋቸው ከሁለት ሚሊዮን ብር በላይ የሚያወጡ የወንዶች ሱሪ፣ ጫማ እና ቲሸርቶችን ሰርቀው ሊሰወሩ ሲሉ ድርጊቱን በተመለከቱ ግለሰቦች እና በፖሊስ አባላት በቁጥጥር ስር ውለዋል፡፡
ፖሊስ በወቅቱ ተጠርጣሪዎቹን በቁጥጥር ስር ባዋለበት ወቅት ባደረገው ፍተሻ ከሌሎች ክፍለ ከተሞች ከሰረቁት የጎማ ጎሚኒ እና የኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ ኬብል ጋር በቁጥጥር ስር ውለው ምርመራ እየተጣራባቸው እንደሚገኝ የልደታ ክ/ከተማ ፖሊስ ዋና መምሪያ ገልጾ ተገቢውን ማስረጃ በማጠናቀር ክስ እንደሚያስመሰርትም አስታውቋል፡፡
የክረምት ወቅት እንደመሆኑ መጠን ጨለማን እና ዝናብን እንደምቹ አጋጣሚ በመጠቀም የሚፈፀሙ ወንጀሎችን ለመከላከል የንግድ ተቋማትም ሆኑ ድርጅቶች የጥበቃ አቅማቸውን ማጠናከር እንደሚጠበቅባቸውም የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ አስታውቋል፡፡
Seledadotio
Seledadotio
Sponsored by
Surafel
9 hours ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) ሰኞ ዕለት በአማራ ክልል በጣለው ከባድ ዝናብ ምክንያት በተከሰተ የመሬት መንሸራተት የ14 ሰዎች ህይወት ሲያልፍ፣ በሰባት ሰዎች ላይ ደግሞ ጉዳት ደርሷል። የፍለጋ እና የነፍስ አድን ስራው አሁንም ቀጥሎ ባለበት በዚህ ወቅት፣ እስካሁን የገቡበት ያልታወቁ እና በፍርስራሹ ስር የተቀበሩ በርካታ ሰዎች እንዳሉ ተነግሯል።
አደጋው የተከሰተው በፃድቃኔ ደብረ ምጥማቅ ቅድስት ማርያም ገዳም ሲሆን፣ በወቅቱ በመቶዎች የሚቆጠሩ ምዕመናን ለፀበል እና ለመንፈሳዊ ፈውስ በስፍራው ተሰብስበው ነበር። የሀገረ ስብከቱ ዋና ስራ አስኪያጅ መጋቤ ሐዲስ ነቃ ጥበብ አባቡ ለአሶሼትድ ፕሬስ እንደተናገሩት፣ "አደጋው የተከሰተው ከጠዋቱ 1፡00 ሰዓት ገደማ ሲሆን፣ ከሟቾቹ መካከል አብዛኞቹ ፀበል ለመጠመቅ የተሰበሰቡ ነበሩ።" ስራ አስኪያጁ አክለውም፣ "ከሟቾቹ መካከል አስራ አንዱ በገዳሙ ውስጥ የተቀበሩ ሲሆን፣ የሌሎቹ አስከሬን ወደ ትውልድ ስፍራቸው ተልኳል፤ ይሁን እንጂ የአንዳንዶቹን ሟቾች ማንነት ለመለየት አስቸጋሪ ሆኗል" ብለዋል።
ከባድ ጉዳት የደረሰባቸው ሰዎች ከገዳሙ 70 ኪሎ ሜትር (43 ማይል) ርቀት ላይ ወደምትገኘው የሰሜን ሸዋ አስተዳደር ዞን ዋና ከተማ ደብረ ብርሃን ለህክምና ተወስደዋል። የመሬት መንሸራተቱ የተከሰተው ከተራራ አጠገብ በመሆኑ፣ ግዙፍ አለቶች ተገንጥለው በምዕመናኑ ላይ መውደቃቸው አደጋውን ይበልጥ አባብሶታል። የአካባቢው አስተዳደር የኮሙኒኬሽን ጽህፈት ቤት ባወጣው መግለጫ፣ የፍለጋ እና አድን ስራዎችን ለማገዝ የአካባቢው የአደጋ መከላከል ጽህፈት ቤት ባለሙያዎች ቡድን ወደ ስፍራው መሰማራቱን አስታውቋል።
በኢትዮጵያ ከሰኔ እስከ መስከረም በሚዘልቀው የክረምት ወቅት ከባድ ዝናብ የሚያስከትለው የመሬት መንሸራተት እና ጎርፍ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተለመደ መጥቷል። በሐምሌ 2024 በደቡብ ኢትዮጵያ በጣለ ከባድ ዝናብ ምክንያት በተከሰተ አሳዛኝ የመሬት መንሸራተት ቢያንስ 257 ሰዎች መሞታቸው ይታወሳል። ከዚህ ቀደምም በዚህ ዓመት መጀመሪያ አካባቢ በደቡብ ኢትዮጵያ፣ ጋሞ ውስጥ በተከሰተ ተመሳሳይ የመሬት መንሸራተት ከ100 በላይ ሰዎች ህይወታቸውን አጥተዋል።
በአፍሪካ ቀንድ የምትገኘው ኢትዮጵያ ከአየር ንብረት ለውጥ ጋር በተያያዙ የከፋ የአየር ፀባይ ክስተቶች በከፍተኛ ሁኔታ እየተጠቃች ትገኛለች። በተለይም በገጠራማ አካባቢዎች ያለው ደካማ መሰረተ ልማት፣ በርካታ ማህበረሰቦችን ለጎርፍ፣ ለመሬት መንሸራተት እና ተደጋጋሚ ድርቅ በቀላሉ ተጋላጭ እንዲሆኑ ያደረጋቸው ሲሆን፣ ለእንደዚህ አይነት አደጋዎች ፈጣን ምላሽ የመስጠት አቅማቸውም እጅግ ውስን ሆኖ ቆይቷል።
አደጋው የተከሰተው በፃድቃኔ ደብረ ምጥማቅ ቅድስት ማርያም ገዳም ሲሆን፣ በወቅቱ በመቶዎች የሚቆጠሩ ምዕመናን ለፀበል እና ለመንፈሳዊ ፈውስ በስፍራው ተሰብስበው ነበር። የሀገረ ስብከቱ ዋና ስራ አስኪያጅ መጋቤ ሐዲስ ነቃ ጥበብ አባቡ ለአሶሼትድ ፕሬስ እንደተናገሩት፣ "አደጋው የተከሰተው ከጠዋቱ 1፡00 ሰዓት ገደማ ሲሆን፣ ከሟቾቹ መካከል አብዛኞቹ ፀበል ለመጠመቅ የተሰበሰቡ ነበሩ።" ስራ አስኪያጁ አክለውም፣ "ከሟቾቹ መካከል አስራ አንዱ በገዳሙ ውስጥ የተቀበሩ ሲሆን፣ የሌሎቹ አስከሬን ወደ ትውልድ ስፍራቸው ተልኳል፤ ይሁን እንጂ የአንዳንዶቹን ሟቾች ማንነት ለመለየት አስቸጋሪ ሆኗል" ብለዋል።
ከባድ ጉዳት የደረሰባቸው ሰዎች ከገዳሙ 70 ኪሎ ሜትር (43 ማይል) ርቀት ላይ ወደምትገኘው የሰሜን ሸዋ አስተዳደር ዞን ዋና ከተማ ደብረ ብርሃን ለህክምና ተወስደዋል። የመሬት መንሸራተቱ የተከሰተው ከተራራ አጠገብ በመሆኑ፣ ግዙፍ አለቶች ተገንጥለው በምዕመናኑ ላይ መውደቃቸው አደጋውን ይበልጥ አባብሶታል። የአካባቢው አስተዳደር የኮሙኒኬሽን ጽህፈት ቤት ባወጣው መግለጫ፣ የፍለጋ እና አድን ስራዎችን ለማገዝ የአካባቢው የአደጋ መከላከል ጽህፈት ቤት ባለሙያዎች ቡድን ወደ ስፍራው መሰማራቱን አስታውቋል።
በኢትዮጵያ ከሰኔ እስከ መስከረም በሚዘልቀው የክረምት ወቅት ከባድ ዝናብ የሚያስከትለው የመሬት መንሸራተት እና ጎርፍ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተለመደ መጥቷል። በሐምሌ 2024 በደቡብ ኢትዮጵያ በጣለ ከባድ ዝናብ ምክንያት በተከሰተ አሳዛኝ የመሬት መንሸራተት ቢያንስ 257 ሰዎች መሞታቸው ይታወሳል። ከዚህ ቀደምም በዚህ ዓመት መጀመሪያ አካባቢ በደቡብ ኢትዮጵያ፣ ጋሞ ውስጥ በተከሰተ ተመሳሳይ የመሬት መንሸራተት ከ100 በላይ ሰዎች ህይወታቸውን አጥተዋል።
በአፍሪካ ቀንድ የምትገኘው ኢትዮጵያ ከአየር ንብረት ለውጥ ጋር በተያያዙ የከፋ የአየር ፀባይ ክስተቶች በከፍተኛ ሁኔታ እየተጠቃች ትገኛለች። በተለይም በገጠራማ አካባቢዎች ያለው ደካማ መሰረተ ልማት፣ በርካታ ማህበረሰቦችን ለጎርፍ፣ ለመሬት መንሸራተት እና ተደጋጋሚ ድርቅ በቀላሉ ተጋላጭ እንዲሆኑ ያደረጋቸው ሲሆን፣ ለእንደዚህ አይነት አደጋዎች ፈጣን ምላሽ የመስጠት አቅማቸውም እጅግ ውስን ሆኖ ቆይቷል።
18 hours ago
በራያ ውጥረት አለ-ነዋሪዎቹ
ከቀናት በፊት በሱዳን አዋሳኝ ሸረሪና በፌደራል ኃይሎች እና በህወሓት ታጣቂዎች መካከል የነበረው ግጭት ጋብ ቢልም፣ በራያ አላማጣ ግንባር በኩል ግን ወታደራዊ ዝግጅቱ እና ፍጥጫው ማየሉን ነዋሪዎች ተናግረዋል። ስማቸው እንዳይጠቀስ የፈለጉ የአላማጣ ከተማ ነዋሪ፣ የህወሓት ሠራዊት በራያ ግንባር በጨርጨር፣በቢሶበር እና ሌሎች አካባቢዎች ተሰማርተዋል ይላሉ።
«ህወሓት ሠራዊቶች ብዙ አርሚዎች በራያ ግንባር አሰማርተዋል። ለጦርነት ዝግጁ እንዲሆኑ መመሪያ ወርዶላቸዋል። ዝግጅት ያለው አሁን በጨርጨር በኩልና ቢሶበር ነው። በዛ ቡታ መርፌ አካባቢ አለ። ከዚህ በዋጃ ቆቦ፣ በጃርሮታ ጀምሮ፣ በዳንያ ለኮ፣ ሰሌን ውኃ፣ በላይ በር በባይባዋ፣ ቁሙጋ ላይ ያለውን አካባቢ ሁሉ ነው ዝግጅቱ። የዋጃን መስመር ተከተሎም የራሳቸውን አርሚ አዘጋጅተዋል።»
መካናይዝድ ጦርም በማንቀሳቀስ ቦታ እያሲያዙ ነው ብለዋል።
አሁን ባለው ወታደራዊ ዝግጅት እና እንቅስቃሴ ጦርነቱ በማንኛውም ጊዜ ሊጀምር ይችላል የሚሉት የራያ ወረዳ ነዋሪ፣ ጦርነቱ በተጀመረ ቁጥር ጉዳት የሚደርስበት የራያ ማኅበረሰብ በእጅጉ ነፃነቱን ይሻል ብለዋል።
Seledadotio
Seledadotio
ከቀናት በፊት በሱዳን አዋሳኝ ሸረሪና በፌደራል ኃይሎች እና በህወሓት ታጣቂዎች መካከል የነበረው ግጭት ጋብ ቢልም፣ በራያ አላማጣ ግንባር በኩል ግን ወታደራዊ ዝግጅቱ እና ፍጥጫው ማየሉን ነዋሪዎች ተናግረዋል። ስማቸው እንዳይጠቀስ የፈለጉ የአላማጣ ከተማ ነዋሪ፣ የህወሓት ሠራዊት በራያ ግንባር በጨርጨር፣በቢሶበር እና ሌሎች አካባቢዎች ተሰማርተዋል ይላሉ።
«ህወሓት ሠራዊቶች ብዙ አርሚዎች በራያ ግንባር አሰማርተዋል። ለጦርነት ዝግጁ እንዲሆኑ መመሪያ ወርዶላቸዋል። ዝግጅት ያለው አሁን በጨርጨር በኩልና ቢሶበር ነው። በዛ ቡታ መርፌ አካባቢ አለ። ከዚህ በዋጃ ቆቦ፣ በጃርሮታ ጀምሮ፣ በዳንያ ለኮ፣ ሰሌን ውኃ፣ በላይ በር በባይባዋ፣ ቁሙጋ ላይ ያለውን አካባቢ ሁሉ ነው ዝግጅቱ። የዋጃን መስመር ተከተሎም የራሳቸውን አርሚ አዘጋጅተዋል።»
መካናይዝድ ጦርም በማንቀሳቀስ ቦታ እያሲያዙ ነው ብለዋል።
አሁን ባለው ወታደራዊ ዝግጅት እና እንቅስቃሴ ጦርነቱ በማንኛውም ጊዜ ሊጀምር ይችላል የሚሉት የራያ ወረዳ ነዋሪ፣ ጦርነቱ በተጀመረ ቁጥር ጉዳት የሚደርስበት የራያ ማኅበረሰብ በእጅጉ ነፃነቱን ይሻል ብለዋል።
Seledadotio
Seledadotio
19 hours ago
የኢትዮጵያ ከ20 ዓመት በታች አትሌቲክስ ቡድን በሰላም ኦሪገን ደርሷል
#ethiopia | በአሜሪካ ኦሪገን ግዛት ዩጂን ከተማ ከሐምሌ 29 እስከ ነሐሴ 3፣ 2018 ዓ.ም በሚካሄደው 21ኛው የዓለም ከ20 ዓመት በታች (World Athletics U20 Championships) የአትሌቲክስ ሻምፒዮና ለመሳተፍ የተጓዘው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ልዑክ ቡድን በሰላም ኦሪገን ደርሷል።
ሻምፒዮናው በዓለም አትሌቲክስ ታሪክ ልዩ ስፍራ ባለው የሄይዋርድ ፊልድ (Hayward Field) ስታዲየም የሚካሄድ ሲሆን፣ ይህ ስታዲየም በርካታ ዓለም አቀፍ ውድድሮችንና ታሪካዊ የአትሌቲክስ ፉክክሮችን በማስተናገድ የታወቀ ነው።
በዘንድሮው ሻምፒዮና ኢትዮጵያ በ5000 ሜትር፣ 3000 ሜትር፣ 1500 ሜትር፣ 800 ሜትር (በሁለቱም ፆታዎች)፣ 3000 ሜትር መሰናክል (በሴቶች)፣ 400 ሜትር (በሴቶች) እና በርምጃ ውድድር (በሁለቱም ፆታዎች) በመሳተፍ ጠንካራ ውጤት ለማስመዝገብ በተጠናከረ ዝግጅት ቀርባለች።
ይህ ውድድር ለወጣት አትሌቶች ዓለም አቀፍ ልምድ የሚያስገኝ እና የወደፊት የኦሎምፒክና የዓለም ሻምፒዮኖች የሚፈጠሩበት አንዱ ትልቅ መድረክ በመሆኑ፣ የኢትዮጵያ ቡድንም የሀገሪቱን የረጅም ርቀት አትሌቲክስ ስኬት ለማስቀጠል ተስፋ ተጥሎበታል።
የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ለመላው ልዑክ ቡድን የተሳካ ውድድርና የድል ጉዞ በመመኘት መልካም ዕድል ብሏል።
መልካም ዕድል ለኢትዮጵያ ቡድን! 🇪🇹
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#ethiopia | በአሜሪካ ኦሪገን ግዛት ዩጂን ከተማ ከሐምሌ 29 እስከ ነሐሴ 3፣ 2018 ዓ.ም በሚካሄደው 21ኛው የዓለም ከ20 ዓመት በታች (World Athletics U20 Championships) የአትሌቲክስ ሻምፒዮና ለመሳተፍ የተጓዘው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ልዑክ ቡድን በሰላም ኦሪገን ደርሷል።
ሻምፒዮናው በዓለም አትሌቲክስ ታሪክ ልዩ ስፍራ ባለው የሄይዋርድ ፊልድ (Hayward Field) ስታዲየም የሚካሄድ ሲሆን፣ ይህ ስታዲየም በርካታ ዓለም አቀፍ ውድድሮችንና ታሪካዊ የአትሌቲክስ ፉክክሮችን በማስተናገድ የታወቀ ነው።
በዘንድሮው ሻምፒዮና ኢትዮጵያ በ5000 ሜትር፣ 3000 ሜትር፣ 1500 ሜትር፣ 800 ሜትር (በሁለቱም ፆታዎች)፣ 3000 ሜትር መሰናክል (በሴቶች)፣ 400 ሜትር (በሴቶች) እና በርምጃ ውድድር (በሁለቱም ፆታዎች) በመሳተፍ ጠንካራ ውጤት ለማስመዝገብ በተጠናከረ ዝግጅት ቀርባለች።
ይህ ውድድር ለወጣት አትሌቶች ዓለም አቀፍ ልምድ የሚያስገኝ እና የወደፊት የኦሎምፒክና የዓለም ሻምፒዮኖች የሚፈጠሩበት አንዱ ትልቅ መድረክ በመሆኑ፣ የኢትዮጵያ ቡድንም የሀገሪቱን የረጅም ርቀት አትሌቲክስ ስኬት ለማስቀጠል ተስፋ ተጥሎበታል።
የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ለመላው ልዑክ ቡድን የተሳካ ውድድርና የድል ጉዞ በመመኘት መልካም ዕድል ብሏል።
መልካም ዕድል ለኢትዮጵያ ቡድን! 🇪🇹
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
20 hours ago
ኢትዮጵያ ለጅቡቲ የጭነት ተሽከርካሪዎች ማረፊያ የሚሆን መሬት ሰጠች
ኢትዮጵያ እና ጅቡቲ በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን የንግድና የትራንስፖርት ኮሪደር ለማዘመን የሚያስችላቸውን ታሪካዊ ስምምነት በመተግበር በሞጆ ከተማ የመሬት ርክክብ ፈጸሙ።
ላለፉት 25 ዓመታት ዘግይቶ የቆየው ይህ ፕሮጀክት፣ ለጅቡቲ የከባድ ጭነት ተሽከርካሪዎች ማቆሚያ ተርሚናል ግንባታ የሚውል መሬት ለጅቡቲ ወገን በመስጠት እውን ሆኗል።
በሞጆ ከተማ በተካሄደው የርክክብ ሥነ-ሥርዓት ላይ የኢትዮጵያ የትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ሚኒስትር ዓለሙ ስሜ፣ የጅቡቲ የመሠረተ ልማትና መሳሪያዎች ሚኒስትር ሳይድ ኑህ ሀሰን፣ የሞጆ ከተማ ከንቲባ እና የሁለቱ ሀገራት ከፍተኛ ባለሥልጣናት ተገኝተዋል።
ዓለሙ ስሜ እንደገለጹት፤ ፕሮጀክቱ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ እና በጅቡቲ ባለሥልጣናት መካከል በተደረገው ውይይት ውሳኔ ያገኘ ሲሆን፣ የሁለቱን ሀገራት ታሪካዊ እና ኢኮኖሚያዊ ቁርኝት የበለጠ ያጠናክራል።
ለባህር በር አልባዋ ኢትዮጵያ ዋነኛ የንግድ መስመር የሆነው የሞጆ-ጅቡቲ ኮሪደር፣ አዲሱ የከባድ መኪኖች ማቆሚያ ተርሚናል ሲገነባበት በትራፊክ መጨናነቅ ምክንያት ይባክን የነበረውን ጊዜና ተጨማሪ ወጪ በእጅጉ ይቀንሰዋል ተብሏል።
በተጨማሪም ኢትዮጵያ እና ጅቡቲን የሚያገናኘውን የባቡር መስመር የጭነት አቅም እስከ እ.ኤ.አ. 2027 ወደ 6.2 ሚሊዮን ቶን ለማሳደግ ታቅዶ እየተሰራ እንደሚገኝ ይታወቃል።
Seledadotio
Seledadotio
ኢትዮጵያ እና ጅቡቲ በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን የንግድና የትራንስፖርት ኮሪደር ለማዘመን የሚያስችላቸውን ታሪካዊ ስምምነት በመተግበር በሞጆ ከተማ የመሬት ርክክብ ፈጸሙ።
ላለፉት 25 ዓመታት ዘግይቶ የቆየው ይህ ፕሮጀክት፣ ለጅቡቲ የከባድ ጭነት ተሽከርካሪዎች ማቆሚያ ተርሚናል ግንባታ የሚውል መሬት ለጅቡቲ ወገን በመስጠት እውን ሆኗል።
በሞጆ ከተማ በተካሄደው የርክክብ ሥነ-ሥርዓት ላይ የኢትዮጵያ የትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ሚኒስትር ዓለሙ ስሜ፣ የጅቡቲ የመሠረተ ልማትና መሳሪያዎች ሚኒስትር ሳይድ ኑህ ሀሰን፣ የሞጆ ከተማ ከንቲባ እና የሁለቱ ሀገራት ከፍተኛ ባለሥልጣናት ተገኝተዋል።
ዓለሙ ስሜ እንደገለጹት፤ ፕሮጀክቱ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ እና በጅቡቲ ባለሥልጣናት መካከል በተደረገው ውይይት ውሳኔ ያገኘ ሲሆን፣ የሁለቱን ሀገራት ታሪካዊ እና ኢኮኖሚያዊ ቁርኝት የበለጠ ያጠናክራል።
ለባህር በር አልባዋ ኢትዮጵያ ዋነኛ የንግድ መስመር የሆነው የሞጆ-ጅቡቲ ኮሪደር፣ አዲሱ የከባድ መኪኖች ማቆሚያ ተርሚናል ሲገነባበት በትራፊክ መጨናነቅ ምክንያት ይባክን የነበረውን ጊዜና ተጨማሪ ወጪ በእጅጉ ይቀንሰዋል ተብሏል።
በተጨማሪም ኢትዮጵያ እና ጅቡቲን የሚያገናኘውን የባቡር መስመር የጭነት አቅም እስከ እ.ኤ.አ. 2027 ወደ 6.2 ሚሊዮን ቶን ለማሳደግ ታቅዶ እየተሰራ እንደሚገኝ ይታወቃል።
Seledadotio
Seledadotio
21 hours ago
(ዘ-ሐበሻ ሕይወት)) አደጋው ከተፈጸመ እነሆ አንድ ወር አልፎታል። የ50 ዓመቷን ኢትዮጵያዊት ሰርክአዲስ አበበ በቀለን ህይወት በከፍተኛ ስካር አሽከርክራ የቀጠፈችው የ28 ዓመቷ ማሪ ባህንድዋ፣ አሁን ላይ እስከ 20 ዓመታት ሊደርስ የሚችል የጽኑ እሥራት ፍርድ ከፊቷ ተደቅኗል። በጆርጂያ ግዛት ህግ መሰረት፣ አንደኛ ደረጃ የተሽከርካሪ ግድያ ብቻውን ከ3 እስከ 15 ዓመት የሚያስቀጣ ሲሆን፣ ከዚህ ጋር የተደራረቡት ሁለት የDUI (በስካር ማሽከርከር) እና የቸልተኝነት ወንጀሎች ሲታከሉበት፣ ማሪ የወጣትነት ዘመኗን ሙሉ በጨለማ የብረት አጥር ውስጥ እንድታሳልፍ ሊያደርጋት ይችላል።
ነገሩን ይበልጥ አሳዛኝ እና ልብ ሰባሪ የሚያደርገው ከግድያው ጀርባ ያለው የአደጋው መነሻ ምክንያት ነው። ማሪ የዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ብሔራዊ ቡድን የነፍስ ደጋፊ ነበረች። አደጋው ከመከሰቱ አንድ ቀን ቀደም ብሎ በአትላንታ ከተማ የተካሄደውን የኮንጎ የዓለም ዋንጫ ጨዋታ ስትከታተል እና በከፍተኛ ስሜት ስታከብር ውላለች። በዚያች ሌሊት በከፍተኛ ስካር ውስጥ ሆና ስታሽከረክረው የነበረው ጂፕ (Jeep Wrangler) መኪናዋ ላይም፣ የኮንጎ ደጋፊ መሆኗን የሚገልጹ ጽሁፎች እና መፈክሮች ተለጥፈውበት ነበር።
የኮንጎን እግር ኳስ ጨዋታ ድምቀት በከፍተኛ የአልኮል ስካር ታጅባ ስታከብር ያመሸችው ማሪ፣ የራሷን የደስታ ምሽት በንጹህ እግረኛ ደም አጥቅራዋለች። በዚያች የጭለማ ሌሊት ኮርትላንድ አቬኑ ላይ መንገዱን በሰላም እያቋረጠች የነበረችው ምስኪን ኢትዮጵያዊት፣ በመኪናዋ ላይ የኮንጎን መፈክር በለጠፈች እና ራሷን መቆጣጠር ባቃታት ሰካራም አሽከርካሪ የህይወት ጉዞዋ በድንገት እና በአሰቃቂ ሁኔታ ተቋጭቷል።
የአንዲት ሀላፊነት የጎደላት ግለሰብ የደስታ ስካር፣ የአንድን ኢትዮጵያዊት ቤተሰብ ለዘለዓለማዊ የሀዘን ማቅ አልብሷል። አሁን ፍርድ ቤቱ ማሪን ከህብረተሰቡ በማግለል ተመጣጣኝ የሆነውን የጽኑ እሥራት ቅጣት ያስተላልፋል ተብሎ በጉጉት የሚጠበቅ ሲሆን፣ ይህ አሳዛኝ ክስተት ግን በስካር የሚመጣ የሰከንድ ስህተት የሁለትን ሰዎች (የገዳይን እና የሟችን) ህይወት እንዴት ለዘለዓለም በጨለማ እንደሚያጠፋው ቁልጭ አድርጎ ያሳየ መሪር ትምህርት ሆኖ አልፏል።
ነገሩን ይበልጥ አሳዛኝ እና ልብ ሰባሪ የሚያደርገው ከግድያው ጀርባ ያለው የአደጋው መነሻ ምክንያት ነው። ማሪ የዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ብሔራዊ ቡድን የነፍስ ደጋፊ ነበረች። አደጋው ከመከሰቱ አንድ ቀን ቀደም ብሎ በአትላንታ ከተማ የተካሄደውን የኮንጎ የዓለም ዋንጫ ጨዋታ ስትከታተል እና በከፍተኛ ስሜት ስታከብር ውላለች። በዚያች ሌሊት በከፍተኛ ስካር ውስጥ ሆና ስታሽከረክረው የነበረው ጂፕ (Jeep Wrangler) መኪናዋ ላይም፣ የኮንጎ ደጋፊ መሆኗን የሚገልጹ ጽሁፎች እና መፈክሮች ተለጥፈውበት ነበር።
የኮንጎን እግር ኳስ ጨዋታ ድምቀት በከፍተኛ የአልኮል ስካር ታጅባ ስታከብር ያመሸችው ማሪ፣ የራሷን የደስታ ምሽት በንጹህ እግረኛ ደም አጥቅራዋለች። በዚያች የጭለማ ሌሊት ኮርትላንድ አቬኑ ላይ መንገዱን በሰላም እያቋረጠች የነበረችው ምስኪን ኢትዮጵያዊት፣ በመኪናዋ ላይ የኮንጎን መፈክር በለጠፈች እና ራሷን መቆጣጠር ባቃታት ሰካራም አሽከርካሪ የህይወት ጉዞዋ በድንገት እና በአሰቃቂ ሁኔታ ተቋጭቷል።
የአንዲት ሀላፊነት የጎደላት ግለሰብ የደስታ ስካር፣ የአንድን ኢትዮጵያዊት ቤተሰብ ለዘለዓለማዊ የሀዘን ማቅ አልብሷል። አሁን ፍርድ ቤቱ ማሪን ከህብረተሰቡ በማግለል ተመጣጣኝ የሆነውን የጽኑ እሥራት ቅጣት ያስተላልፋል ተብሎ በጉጉት የሚጠበቅ ሲሆን፣ ይህ አሳዛኝ ክስተት ግን በስካር የሚመጣ የሰከንድ ስህተት የሁለትን ሰዎች (የገዳይን እና የሟችን) ህይወት እንዴት ለዘለዓለም በጨለማ እንደሚያጠፋው ቁልጭ አድርጎ ያሳየ መሪር ትምህርት ሆኖ አልፏል።
23 hours ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የዩናይትድ ኪንግደም የባህር ንግድ ኦፕሬሽን ማዕከል እንዳስታወቀው፣ ዛሬ [በአካባቢው አቆጣጠር] ማክሰኞ ማለዳ ላይ በኦማን የባህር ዳርቻ አቅራቢያ የምትጓዝ አንዲት የጭነት መርከብ ባልታወቀ ተወንጫፊ መሳሪያ መመታቷን ሪፖርት አድርጋለች። ተቋሙ እንዳብራራው፣ መርከቧ ከኦማኗ ኻሳብ ከተማ በስተሰሜን ምስራቅ 20 የባህር ማይል ርቀት ላይ እየተጓዘች ባለችበት ወቅት ጥቃት እንደደረሰባት በVHF ቻናል 16 የድረሱልኝ ጥሪ አስተላልፋለች።
ይህንን ክስተት ተከትሎ ባለስልጣናት ምርመራ የጀመሩ ሲሆን፣ ዩኬ ኤም ቲ ኦ በቀጠናው የሚያልፉ መርከቦች ከፍተኛ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ እና ማንኛውንም አጠራጣሪ እንቅስቃሴ ለሚመለከተው አካል ሪፖርት እንዲያደርጉ አሳስቧል። እስካሁን ድረስ ለዚህ ጥቃት ኃላፊነት የወሰደ አካል የለም።
ይህ የጥቃት ክስተት የተሰማው፣ በቅርቡ በአሜሪካ እና በኢራን መካከል የተፈጠረውን ወታደራዊ ፍጥጫ ተከትሎ በሆርሙዝ ባህረ ሰላጤ ዙሪያ ውጥረቱ አይሎ ባለበት ወቅት ነው። ዋሽንግተን በዚሁ ስትራቴጂካዊ የውሃ መስመር ላይ የባህር ላይ ጉዞ ነፃነት እንዲረጋገጥ ለቴህራን ጥሪ ስታቀርብ፣ ኢራን በበኩሏ በባህር ዳርቻዎቿ አቅራቢያ የሚደረጉ የመርከብ እንቅስቃሴዎች በእሷ ቁጥጥር እና እይታ ስር መሆን አለባቸው የሚል ጠንካራ አቋም እያንጸባረቀች ትገኛለች።
ባለፈው ቅዳሜ የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በቀጠናው በተደረገ የሽምግልና ጥረት ምክንያት በኢራን ላይ ሊፈጽሙት የነበረውን ወታደራዊ ጥቃት መሰረዛቸውን መግለጻቸው ይታወሳል። ይሁን እንጂ የኢራን ባለስልጣናት ይህን የፕሬዝዳንቱን ንግግር ውድቅ በማድረግ፣ የሆርሙዝ ባህረ ሰላጤን ዳግም ክፍት ለማድረግ የተደረሰ ምንም ዓይነት ስምምነት የለም ሲሉ ሪፖርቶቹን አስተባብለዋል።
ይህንን ክስተት ተከትሎ ባለስልጣናት ምርመራ የጀመሩ ሲሆን፣ ዩኬ ኤም ቲ ኦ በቀጠናው የሚያልፉ መርከቦች ከፍተኛ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ እና ማንኛውንም አጠራጣሪ እንቅስቃሴ ለሚመለከተው አካል ሪፖርት እንዲያደርጉ አሳስቧል። እስካሁን ድረስ ለዚህ ጥቃት ኃላፊነት የወሰደ አካል የለም።
ይህ የጥቃት ክስተት የተሰማው፣ በቅርቡ በአሜሪካ እና በኢራን መካከል የተፈጠረውን ወታደራዊ ፍጥጫ ተከትሎ በሆርሙዝ ባህረ ሰላጤ ዙሪያ ውጥረቱ አይሎ ባለበት ወቅት ነው። ዋሽንግተን በዚሁ ስትራቴጂካዊ የውሃ መስመር ላይ የባህር ላይ ጉዞ ነፃነት እንዲረጋገጥ ለቴህራን ጥሪ ስታቀርብ፣ ኢራን በበኩሏ በባህር ዳርቻዎቿ አቅራቢያ የሚደረጉ የመርከብ እንቅስቃሴዎች በእሷ ቁጥጥር እና እይታ ስር መሆን አለባቸው የሚል ጠንካራ አቋም እያንጸባረቀች ትገኛለች።
ባለፈው ቅዳሜ የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በቀጠናው በተደረገ የሽምግልና ጥረት ምክንያት በኢራን ላይ ሊፈጽሙት የነበረውን ወታደራዊ ጥቃት መሰረዛቸውን መግለጻቸው ይታወሳል። ይሁን እንጂ የኢራን ባለስልጣናት ይህን የፕሬዝዳንቱን ንግግር ውድቅ በማድረግ፣ የሆርሙዝ ባህረ ሰላጤን ዳግም ክፍት ለማድረግ የተደረሰ ምንም ዓይነት ስምምነት የለም ሲሉ ሪፖርቶቹን አስተባብለዋል።
Sponsored by
Surafel
1 day ago
ፋሻ ላውንጅ ሀዋሳ
– የመዝናኛዎ አዲሱ መዳረሻ!
ሀዋሳን በልዩ መንገድ ለመዝናናት ይፈልጋሉ?
ፋሻ ላውንጅ ሀዋሳ ለከተማው ነዋሪዎች ብቻ ሳይሆን ከየትኛውም ስፍራ ለሚመጡ እንግዶች የተለየ የመዝናኛ ልምድ ያቀርባል።
🌴 ነፋሻማና ዘመናዊ አካባቢ
🎧 በምርጥ ዲጄዎች የተሞላ አስደሳች ሙዚቃ
🍽️ ጣፋጭ ምግቦችና የተለያዩ መጠጦች
🤝 ፈጣንና ሙያዊ አገልግሎት
✨ ለወዳጅ ስብሰባ፣ ለቤተሰብ መዝናኛ እና ለልዩ ዝግጅቶች ተስማሚ
ደማቅ ቀንም ሆነ አስደሳች ምሽት በሀዋሳ ማሳለፍ ከፈለጉ፣ ፋሻ ላውንጅ የመጀመሪያ ምርጫዎ ነው።
አድራሻ: ሀዋሳ 05፣ ከጉዱማሌ ፊት ለፊት
ስልክ +251-916-860330
ፋሻ ላውንጅ ሀዋሳ
ይምጡ... ይዝናኑ... የማይረሳ ትዝታ ይዘው ይመለሱ!
– የመዝናኛዎ አዲሱ መዳረሻ!
ሀዋሳን በልዩ መንገድ ለመዝናናት ይፈልጋሉ?
ፋሻ ላውንጅ ሀዋሳ ለከተማው ነዋሪዎች ብቻ ሳይሆን ከየትኛውም ስፍራ ለሚመጡ እንግዶች የተለየ የመዝናኛ ልምድ ያቀርባል።
🌴 ነፋሻማና ዘመናዊ አካባቢ
🎧 በምርጥ ዲጄዎች የተሞላ አስደሳች ሙዚቃ
🍽️ ጣፋጭ ምግቦችና የተለያዩ መጠጦች
🤝 ፈጣንና ሙያዊ አገልግሎት
✨ ለወዳጅ ስብሰባ፣ ለቤተሰብ መዝናኛ እና ለልዩ ዝግጅቶች ተስማሚ
ደማቅ ቀንም ሆነ አስደሳች ምሽት በሀዋሳ ማሳለፍ ከፈለጉ፣ ፋሻ ላውንጅ የመጀመሪያ ምርጫዎ ነው።
አድራሻ: ሀዋሳ 05፣ ከጉዱማሌ ፊት ለፊት
ስልክ +251-916-860330
ፋሻ ላውንጅ ሀዋሳ
ይምጡ... ይዝናኑ... የማይረሳ ትዝታ ይዘው ይመለሱ!
1 day ago
(ዘ-ሐበሻ ሕይወት) በአዲስ አበባ ከተማ ሰማይ ላይ የተፈጠረው ያልተጠበቀ መጥፎ የአየር ፀባይ፣ በከባድ ሀዘን ላይ ለሚገኝ አንድ የዚምባብዌ ቤተሰብ ተጨማሪ ሰቆቃ እና እንግልት ሆኖ አልፏል። ከእንግሊዝ ሀገር ተነስቶ በአዲስ አበባ በኩል ወደ ዚምባብዌ ቡላዋዮ ከተማ የሶስት የቤተሰብ አባላትን አስከሬን አሳፍሮ ሲጓዝ የነበረ አውሮፕላን፣ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ማረፍ ባለመቻሉ ወደ ጅቡቲ አቅጣጫውን ለመቀየር ተገዷል።
በዚህ ያልተጠበቀ ክስተት ምክንያት፣ አውሮፕላኑ ወደ ዚምባብዌ ከሚጓዘው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ጋር ሊያደርገው የነበረውን የበረራ ግንኙነት (Connecting flight) ስቷል። ትናንት እሁድ አስከሬኖቹን ለመቀበል በጉጉት እና በሀዘን ሲጠባበቁ የነበሩት የኩማሎ ቤተሰቦች፣ የበረራው መስተጓጎል እና አስከሬኖቹ በዕለቱ እንደማይደርሱ ሲነገራቸው ዳግም በሀዘን ተስብረዋል።
ሟቾቹ የ42 ዓመቷ እናት ኖታቦ ዛንዲሌ ቹማ እና በዩናይትድ ኪንግደም የተወለዱት ሁለት ሴት ልጆቿ፣ ናታሊ እና ናላ ናቸው። ባለፈው ጁላይ 3 በዩናይትድ ኪንግደም ቤድፎርድሻየር በሚገኘው መኖሪያ ቤታቸው ውስጥ ተገድለው መገኘታቸው፣ ዚምባብዌያውያንን እና የእንግሊዝን ማህበረሰብ ክፉኛ ያስደነገጠ አሳዛኝ ክስተት ነበር። የእናት እና የልጆቿ አስከሬን ወደ ሀገራቸው ተመልሶ አብረው እንዲያርፉ የብሪታንያ ባለስልጣናት ፈቃድ የሰጡት ባለፈው ሳምንት ነበር።
የቤተሰቡ ቃል አቀባይ ሊዮን ሊሮይ ኩማሎ፣ በኢትዮጵያ በገጠመው አስከፊ የአየር ፀባይ ምክንያት ጉዞው ቢስተጓጎልም አሁን ላይ ሁሉም ነገር ተስተካክሎ አስከሬኖቹ ሰኞ ዕለት ሀራሬ በሚገኘው ሮበርት ገብርኤል ሙጋቤ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ እንደሚደርሱ አረጋግጠዋል። አስከሬኖቹ ከመዲናዋ ሀራሬ በየብስ ትራንስፖርት ወደ ቡላዋዮ ተወስደው ማክሰኞ ዕለት በ"ብሉይ ሉቬቬ" የመቃብር ስፍራ ጎን ለጎን ያርፋሉ ተብሎ ይጠበቃል።
ይህ የጉዞ መዘግየት በቤተሰቡ ላይ ተጨማሪ ሀዘን ቢፈጥርም፣ የቡላዋዮ ከተማ የጓባላንዳ ሰፈር ነዋሪዎች ግን ከቤተሰቡ ጎን በመሆን በማታ የጸሎት ፕሮግራሞች ላይ እየተገኙ መጽናናትን እየሰጡ ይገኛሉ።
የነዚህን ንጹሃን ህይወት በማጥፋት የተጠረጠረው የልጆቹ አባት እና የሟች ባል የሆነው ትውልደ ዚምባብዌያዊው የብሪታንያ ዜጋ ዶዳና ምካንዪሲ ቹማ ነው። ግለሰቡ ከግድያው በኋላ አምልጦ በደቡብ አፍሪካ ጆሃንስበርግ በቁጥጥር ስር ውሏል። በአሁኑ ወቅት የብሪታንያ ባለስልጣናት በሶስት የነፍስ ማጥፋት ወንጀሎች ክስ ሊመሰርቱበት አሳልፎ እንዲሰጣቸው ጥረት እያደረጉ ይገኛሉ።
በዚህ ያልተጠበቀ ክስተት ምክንያት፣ አውሮፕላኑ ወደ ዚምባብዌ ከሚጓዘው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ጋር ሊያደርገው የነበረውን የበረራ ግንኙነት (Connecting flight) ስቷል። ትናንት እሁድ አስከሬኖቹን ለመቀበል በጉጉት እና በሀዘን ሲጠባበቁ የነበሩት የኩማሎ ቤተሰቦች፣ የበረራው መስተጓጎል እና አስከሬኖቹ በዕለቱ እንደማይደርሱ ሲነገራቸው ዳግም በሀዘን ተስብረዋል።
ሟቾቹ የ42 ዓመቷ እናት ኖታቦ ዛንዲሌ ቹማ እና በዩናይትድ ኪንግደም የተወለዱት ሁለት ሴት ልጆቿ፣ ናታሊ እና ናላ ናቸው። ባለፈው ጁላይ 3 በዩናይትድ ኪንግደም ቤድፎርድሻየር በሚገኘው መኖሪያ ቤታቸው ውስጥ ተገድለው መገኘታቸው፣ ዚምባብዌያውያንን እና የእንግሊዝን ማህበረሰብ ክፉኛ ያስደነገጠ አሳዛኝ ክስተት ነበር። የእናት እና የልጆቿ አስከሬን ወደ ሀገራቸው ተመልሶ አብረው እንዲያርፉ የብሪታንያ ባለስልጣናት ፈቃድ የሰጡት ባለፈው ሳምንት ነበር።
የቤተሰቡ ቃል አቀባይ ሊዮን ሊሮይ ኩማሎ፣ በኢትዮጵያ በገጠመው አስከፊ የአየር ፀባይ ምክንያት ጉዞው ቢስተጓጎልም አሁን ላይ ሁሉም ነገር ተስተካክሎ አስከሬኖቹ ሰኞ ዕለት ሀራሬ በሚገኘው ሮበርት ገብርኤል ሙጋቤ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ እንደሚደርሱ አረጋግጠዋል። አስከሬኖቹ ከመዲናዋ ሀራሬ በየብስ ትራንስፖርት ወደ ቡላዋዮ ተወስደው ማክሰኞ ዕለት በ"ብሉይ ሉቬቬ" የመቃብር ስፍራ ጎን ለጎን ያርፋሉ ተብሎ ይጠበቃል።
ይህ የጉዞ መዘግየት በቤተሰቡ ላይ ተጨማሪ ሀዘን ቢፈጥርም፣ የቡላዋዮ ከተማ የጓባላንዳ ሰፈር ነዋሪዎች ግን ከቤተሰቡ ጎን በመሆን በማታ የጸሎት ፕሮግራሞች ላይ እየተገኙ መጽናናትን እየሰጡ ይገኛሉ።
የነዚህን ንጹሃን ህይወት በማጥፋት የተጠረጠረው የልጆቹ አባት እና የሟች ባል የሆነው ትውልደ ዚምባብዌያዊው የብሪታንያ ዜጋ ዶዳና ምካንዪሲ ቹማ ነው። ግለሰቡ ከግድያው በኋላ አምልጦ በደቡብ አፍሪካ ጆሃንስበርግ በቁጥጥር ስር ውሏል። በአሁኑ ወቅት የብሪታንያ ባለስልጣናት በሶስት የነፍስ ማጥፋት ወንጀሎች ክስ ሊመሰርቱበት አሳልፎ እንዲሰጣቸው ጥረት እያደረጉ ይገኛሉ።
1 day ago
ደህንነት ነኝ በማለት የማጭበርበር ወንጀል ሲፈፅም የነበረው ግለሰብ በእስራት እና በገንዘብ ተቀጣ
በአምቦ ከተማ ውስጥ ደህንነት ነኝ በማለት የማጭበርበር ወንጀል ሲፈፅም የነበረው ግለሰብ በእስራት እና በገንዘብ መቀጣቱ ተገልጿል ።የአምቦ ከተማ ፖሊስ ዋና መምሪያ የኮሚኒኬሽን ፅ/ቤት ሃላፊ ረዳት ኢንስፔክተር አቡሽ ማሞ ለብስራት ሬዲዮ እንደገለፁት ተከሳሽ ዘሪሁን ጉርሙ የሰላሳ ዓመት ግለሰብ ነው።
በከተማዋ ውስጥ በመዘዋወር " እኔ ደህንነት ነኝ " በወንጀል የተጠረጠሩ ሰዎችን አስፈታለሁ በማለት የማጭበርበር ወንጀል ፈፅሟል።ተከሳሹ አንዲት የአምቦ ከተማ ነዋሪ የሆነች ግለሰብን ባለቤትሽን ከተጠረጠረበት የወንጀል ድርጊት ነፃ እንዲወጣ አደርጋለሁ በማለት ከግለሰቧ ላይ 120 ሺህ ብር ሲቀበል በቁጥጥር ስር ውሏል ።
ፖሊስም በተከሳሹ ላይ አስፈላጊውን የምርመራ መዝገብ በተገቢው ማስረጃ በማጠናከር ለአቃቤህግ ልኳል። አቃቤ ህግም ከፖሊስ የተላከውን የምርመራ መዝገብ ተመልክቶ በአታላይነት ወንጀል ክስ መስርቶበታል።ክሱን የተመለከተው የአምቦ ከተማ ወረዳ ፍርድ ቤት ሃምሌ 17 ቀን 2018 ዓ.ም በዋለው ችሎት ተከሳሽ ዘሪሁን ጉርሙ የራሱን ማንነትና ሁኔታ በመሰወር፣ አሳሳች ነገሮችን በመናገር እና ደህንነት ነኝ በማለት በፈፀመው የማጭበርበር ወንጀል ጥፋተኛ መሆኑ ተረጋግጧል ።
በዚህም መሰረት በሁለት ዓመት ከ9ወር እስራትና በአንድ ሺህ ብር የገንዘብ መቀጮ ፣ እንዲቀጣ የተወሰነበት መሆኑን ረዳት ኢንስፔክተር አቡሽ ማሞ ጨምረው ለብስራት ሬዲዮ ገልፀዋል።
Seledadotio
Seledadotio
በአምቦ ከተማ ውስጥ ደህንነት ነኝ በማለት የማጭበርበር ወንጀል ሲፈፅም የነበረው ግለሰብ በእስራት እና በገንዘብ መቀጣቱ ተገልጿል ።የአምቦ ከተማ ፖሊስ ዋና መምሪያ የኮሚኒኬሽን ፅ/ቤት ሃላፊ ረዳት ኢንስፔክተር አቡሽ ማሞ ለብስራት ሬዲዮ እንደገለፁት ተከሳሽ ዘሪሁን ጉርሙ የሰላሳ ዓመት ግለሰብ ነው።
በከተማዋ ውስጥ በመዘዋወር " እኔ ደህንነት ነኝ " በወንጀል የተጠረጠሩ ሰዎችን አስፈታለሁ በማለት የማጭበርበር ወንጀል ፈፅሟል።ተከሳሹ አንዲት የአምቦ ከተማ ነዋሪ የሆነች ግለሰብን ባለቤትሽን ከተጠረጠረበት የወንጀል ድርጊት ነፃ እንዲወጣ አደርጋለሁ በማለት ከግለሰቧ ላይ 120 ሺህ ብር ሲቀበል በቁጥጥር ስር ውሏል ።
ፖሊስም በተከሳሹ ላይ አስፈላጊውን የምርመራ መዝገብ በተገቢው ማስረጃ በማጠናከር ለአቃቤህግ ልኳል። አቃቤ ህግም ከፖሊስ የተላከውን የምርመራ መዝገብ ተመልክቶ በአታላይነት ወንጀል ክስ መስርቶበታል።ክሱን የተመለከተው የአምቦ ከተማ ወረዳ ፍርድ ቤት ሃምሌ 17 ቀን 2018 ዓ.ም በዋለው ችሎት ተከሳሽ ዘሪሁን ጉርሙ የራሱን ማንነትና ሁኔታ በመሰወር፣ አሳሳች ነገሮችን በመናገር እና ደህንነት ነኝ በማለት በፈፀመው የማጭበርበር ወንጀል ጥፋተኛ መሆኑ ተረጋግጧል ።
በዚህም መሰረት በሁለት ዓመት ከ9ወር እስራትና በአንድ ሺህ ብር የገንዘብ መቀጮ ፣ እንዲቀጣ የተወሰነበት መሆኑን ረዳት ኢንስፔክተር አቡሽ ማሞ ጨምረው ለብስራት ሬዲዮ ገልፀዋል።
Seledadotio
Seledadotio
1 day ago
“ታሪክ በትዝታ ላይ የተጫነ ሸክም አይደለም-የነፍስ መገለጥ እንጂ”
ጋዜጠኛ ዮናስ አየለ እንደጻፈው
ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ ከአሚኮ ጋር ያደረጉትን ቃለምልልስ አዳምጬ እንደጨረስኩ በቃለ ምልልሱ በርዕሰ ጉዳይ ደረጃ ጎልተው ከወጡ ዋና ዋና ጭብጦች መካከል አንዱ ነገረ ታሪክ እንደሆነ ተሰምቶኛል፡፡ ታሪክ-የሀገር ውስጥና የውጭ፤ የሩቅና የቅርብ ዘመን! ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቃለ ምልልሳቸው ያንጸባረቁትን ሚዛናዊና አምክኖአዊ የታሪክ እይታና ድምዳሜያቸውን አለማድነቅ ንፉግነት ነው፡፡ የአሥራ ዘጠነኛው ክፍለ ዘመን እንግሊዛዊ የታሪክ ጸሐፊና ፖለቲከኛ ሎርድ አክተን “History is not a burden on the memory but an illumination of the soul” ብሎ ሲጽፍ “ታሪክ የነፍስ መገለጥ እንጂ በትዝታ ላይ የተጫነ ሸክም አይደለም” ማለቱ ነበር፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቃለ ምልልሳቸው ያነሷቸው የታሪክ አንኳር ጉዳዮች እስከዛሬ ድረስ በሀገራችን የታሪክ አጻጻፍ(Historiography) እና በሕዝባዊ ትርክቶቻችን(በሚዲያዎችን ጭምር) በሚገባቸው ልክ ያልተወሱ፤ ቢወሱም ፈራ ተባ እየተባሉ የሚጠቀሱ፤ አለፍሲልም ባልተገባ የፖለቲካ እይታ ደንቃራ ተደርገው የተወሰዱ የታሪክ ግርዶሽ(eclipse of the history) ሆነው የኖሩ ስብራቶቻችን ነበሩ፡፡ ከነዚህ ቁልፍ ጉዳዮች መካከል ዋነኛዎቹ አንዱ የሕዝቦች ትስስር እና መስተጋብር ታሪክ ሲሆን ሌላኛው በአገረ መንግስት ምሥረታ ውስጥ የሸዋ ጂኦ-ስትራቴጂካዊ ሚናን የተመለከቱት ናቸው፡፡
በመጀመሪያ የአማራና የኦሮሞ ሕዝቦች በኩታ ገጠም ቀዬዎቻቸው እና የታሪክ እድል በፈጠረላቸው የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚና የባህል አጋጣሚዎች እንደሌሎች ማህበረሰቦች ሁሉ መጋባት መዋለዳቸው፤መተሳሰር መዋሀዳቸው ሀቅ የመሆኑን ያህል የታሪክ ጥናት እና የትርክቶቻችን ማጠንጠኛ አለመሆናቸው ይታወቃል፡፡ ከዚህ በባሰ ሁኔታ ደግሞ በነገሥታቱ መካከል የነበረው የፖለቲካ ጋብቻና የመሪዎቻችን ማህበራዊ መሠረት ጉዳይ ነውር እስኪመስል በእውነታው ልክ ሳይጠናና፣ሳይነገርለት ዘመናት አልፈዋል ፡፡ በሌላ በኩል በሸዋና አካባቢው ለረዥም ዘመን የኖሩ ሕዝቦች በአገረ መንግሥት ግንባታ ሂደት የተጫወቱት ሚናና የሚጋሩት ቀደምት የሥልጣኔ ባለቤትነት (ታሪክ ሰሪነት-Agency) ግጥምጥሞሽ በሀገር መሪ ደረጃ መወሳታቸው እጅግ ጉልህ ፋይዳ ያለው ጉዳይ ነው ፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቃለ ምልልሳቸው ያነሷቸው የታሪክ እውነታዎች ያለጥርጥር ታሪካችንንና የታሪክ ምልከታችንን ደጋግመን መመርምር እንዳለብን የሚያስገነዝቡና የወገንተኝነት ጥያቄ በሚነሳባቸው ሃይማኖታዊ የታሪክ ምንጮች እንኳን የተቀመጡ ገሃድ እውነታዎች ናቸው፡፡ መመርመር ለሚፈልግ አጥኚ እነዚህ የታሪክ እውነታዎች በየነገሥታቱ ዜና መዋዕሎች (የዐጼ አምደ ጽዮን፣ ዐጼ ሱስንዮስ፣የዐጼ ገላውዲዮስ፣ የዐጼ ሠርጸ ድንግል ወዘተ)፤ የሃይማኖት ሰነዶች፣ የታሪከ ነገሥት ቅጂዎች፣ ወደ ኢትዮጵያ መጥተው የነበሩ አውሮፓውያን ተጓዦችና ጸሐፊያን (ፍራንስስኮ አልቫሬዝ፣ ፔድሮ ፔዝ፣ ማኑኤል አልሜዳ፣ ጄሮኒሞ ሎቦ፣ ጀምስ ብሩስ፣ ኮንቲ ሮሲኒ ወዘተ ) መዝግበው በተውልን ሰነዶች ሰፍረው የምናገኛቸው፤ ከትውልድ ወደ ትውልድ ሲተላለፉ የኖሩ ቱባ መረጃዎች ናቸው፡፡
ፍራንሲስኮ አልቫሬዝ የተወልን የጽሑፍ ሰነድና ሌሎች ሀገርኛ የቃል መረጃ ምንጮች ዐፄ ልብነድንግል(1498-1532 ዓ.ም.) እንደ መሪ የአማራና የኦሮሞ ብቻ ሳይሆን ምናልባትም የሌሎች ሕዝቦችም ማህበራዊ ዳራ የነበራቸው ንጉሠ ነገሥት እንደሆኑ የሚያስረዱ ሲሆን አልቫሬዝ የንጉሱ የእናት ወንድም የነበሩት አጎታቸው ዶሪ ባህረ ነጋሽ ኦሮሞ እንደነበሩና ባህረ ነጋሽ ዶሪ ሲሞቱ ሥልጣኑ በቀጥታ ወደልጃቸው ቡሎ መሸጋገሩን ጭምር በአይኑ ያየውን ጽፏል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ በትኩረት መታየት የሚገባው ጉዳይ ስለዐጼ ልብነ ድንግል የጦር አዛዦች የተነገሩ የቃል መረጃዎች ናቸወ፡፡ ከእነዚህ መካከል የንጉሠ ነገሥቱ ሠራዊት የቦረንትቻ ባሕል ያውቅ እንደነበር በተክለጻዲቅ መኩሪያ መጻፉና ከዐጼ ልብነድንግል የጦር አዛዦች አንዱ የነበረው ቱሉ ደገልሀን በመራው ከኢማም አሕመድ ጋር የተካሄደ ጦርነት የዐጼው ጦር ሲያፈገፍግ ንጉሠ ነገሥቱ “ሁሉም ቢፈራ ቱሉ እንዴት ፈራ? ” ማለታቸው ስለሠራዊታቸው ሥብጥር የሚነግረን ነገር አለ፡፡
ኦቶማን ቱርኮችን እና የዘመኑ ተላላኪዎቻቸውን ለመዋጋት የንጉሠ ነገሥቱ ሠራዊት አንድ አካል ሆነው እስከ ኤርትራ ድረስ ዘምተው ስለነበሩ የኦሮሞ ተዋጊዎች ተጋድሎ የዐጼ ሠርጸድንግል(1542-1590 ዓ.ም.) ዜና መዋእል በግልጽ አስፍሯል፡፡ እነዚህ የኦሮሞና የሌሎች ሕዝቦች ተወላጅ ወታደሮች ትግራይ እንጢጮ አካባቢ ያካሄዱትን አውደ ውጊያ ዜና መዋዕሉ ይተርካል፡፡ ለመንግሥታቸውና ለሀገራቸው እስከባሕር ጠረፍ ድረስ ዘምተው ዋጋ መክፈላቸውም ተመዝግቧል፡፡ የዐጼ ሱስንዮስ(1607-1632 ዓ.ም.) ዜና መዋእል እና በዘመኑ ኢትዮጵያ መጥተው የነበሩ የአውሮፓ(የፖርቱጋል) ተጓዦች የጻፏቸው የመረጃ ምንጮች ንጉሠ ነገሥቱ ግንደበረት፣ሐምቦና አካባቢው ቤታቸው እንደነበር፤ አጎታቸው ለማሞ እንደሚባል፣ ወላጅ እናታቸው(ሐመልማል ወርቅ) የአዛዥ ኩሎ ልጅ የነበረች፤ የዚሁ የሐመልማል ወርቅ ጎሳ ተወላጅ የሆነ ቡኮ የተባለ ኦሮሞና ሠራዊቱ ለአባይ ቅርብ የሆነች ምዕራብ ሸዋ ላይ ዐጼ ሱስንዮስ ሲያገኙት የነበረውን ደስታና የፍቅሩን ጽናት ዜና መዋዕሉ ሳይሰስት ጽፎታል፡፡ ዐጼ ፋሲል(ከ1632 እስከ 1667 ዓ.ም.) አባቱ ሱስንዮስ እናቱ የወሎ ቃሉ ሰው(እቴጌ ሥልጣን ሞገሳ የሚል ስም የተሰጣት) እንደሆነች የታሪክ ምንጮች ያስረዱናል፡፡ በ1620ዎቹ ዓመታት ጀምሮ በኢትዮጵያ ይኖር የነበረው ፖርቱጋላዊ ቄስ ጄሮኒሞ ሎቦ ስለዐጼ ፋሲል እናትና ኦሮሞ ዘመዶቻቸው በአይን ምስክርነት የሚያውቀውን ጽፏል፡፡ የእቴጌ ሥልጣን ሞገሳ አያት ስለብዝሀ ሃይማኖት አስፈላጊነት የነበራቸውን ግልጽ ፖሊሲ ጭምር ሎቦ ዘግቦታል፡፡ የዐጼ በካፋ(1721-1730 ዓ.ም.) እና የዐጼ ኢዮአስ(1747-1761 ዓ.ም.) ጎንደር መቼም ለሕዝቦች ውህደትና ትስስር ጥሩ ማሳያ ነበረች፡፡ የየጁ ኦሮሞ ገዢ የነበረው የአሚቶ ሴት ልጅ ዝነኛዋ ውቢት ልጇ ዐጼ አዮአስ ነበር፡፡ ኢዮአስ ከኦሮሞ አጎቱ ከደጃች ሉቦ ጋር ሥልጣኑን በጎንደር እንዴት እንዳጸና፤ የቤተ መንግሥቱም የሥራ ቋንቋ አፋን ኦሮሞ እንደነበረ የንጉሠ ነገሥቱ ዜና መዋዕልና በጀምስ ብሩስ ቅጽ ሁለት መጽሀፍ የተመዘገቡ የታሪክ መረጃዎች ያስረዱናል፡፡
መነሻውን ወሎ በማድረግ ጎንደር ጸንቶ የኖረው የየጁ ሥርወ መንግሥት(ወረ ሼኮች) መሥራቾች የመርሳው አባ ጌትዬ፣ የልጃቸው ጓንጉል አባ ሴሩ እንዲሁም የልጅ ልጃቸው የራስ አሊ ጓንጉል(አሊ ትልቁ) ታሪክ በኢዮአስ ዜና መዋዕል፣ በጀምስ ብሩስ መጽሐፍና በሌሎች በርካታ ሰነዶች ታሪካቸው ተዘግቧል፡፡ በኋላ ላይ በሽፈራው በቀለ(ፕሮፌሰር) እና ሞላ ትኩዬ የቀረቡ ጥልቅ ጥናቶች ይህን እውነት በዝርዝር ያስረዱናል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቃለ ምልልሳቸው እንደጠቀሱት የእነዚህ መሪዎች የፖለቲካ ጋብቻ ታሪክ የሚያሳየን በሄዱበት አገር ሁሉ የሕዝቦች ትሥሥር እና የፖለቲካ ጋብቻ የኖረ ታሪካችን እና የጉልበታችን ምንጭ እንደነበረ ነው፡፡ በዳግማዊ ዐጼ ቴዎድሮስ ዘመን የተጻፉ የታሪክ ሰነዶች የወሎዋ ገዢ ወርቂቱ ወዳጆ(የማመዶች ሥርወ መንግሥት መሪ የኢማም አሊ አባ ቡላ ባለቤት) ንጉሥ ምኒልክ ከመቅደላ እስር ቤት እንዲያመልጡ ያደረጉ፤ አጃቢ ሠራዊት አሰማርተው ምኒልክን እስከሸዋ የሸኙ እንደነበሩ በዋናነት ከጸሓፌ ትእዛዝ ገብረ ሥላሴ ታሪከ ዘመን ዘ ዳግማዊ ምኒልክ ዜና መዋዕል እና በመቅደላ አምባ እስር ላይ የነበሩ አውሮፓውያን ከጻፏቸው መረጃዎች እንረዳለን፡፡
ሥልጣኔዎቻችን ሁሉ ተደምረን ያሳካናቸው እንደሆነ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቃለ ምልልሳቸው አንስተዋል፡፡ የዐድዋ ዘመቻና ድሉ ለዚህ አንዱ ማሳያ እንደሆነ ተጨባጭ የታሪክ ምንጮች ያስረዱናል፡፡ በ1888 ዓ.ም. ለዓድዋ ዘመቻ ከመላው ኢትዮጵያ የተመመው ሠረዊት ወፍላ ላይ የነበረው ሠልፍ የንጉሠ ነገሥቱ ዜና መዋዕል እንኳን እንዲህ ይገልጸዋል፡፡ “የመኳንንቱ የጦር መሣሪያ፣ወርቁ፣ ጣፋ፣ ብሩ፣ ሙጣው፣ ጫሜው፣ ሎሚታውና ኩፊታው፣ ከሌቻው፣ ወርቅ ለምዱ እንደጸሐይ ሲያበራ ዋለ፡፡” እንደጸሐይ የበራውን ሕብረ ባሕልና ሕብረ ማንነት ትርክቶቻችን በልኩ አጉልተው ያውቃሉ?
ሸዋና አካባቢው(ወሎን ጨምሮ) እንደ አንድ ጂዞ ስትራቴጂ ሥፍራ የሕዝቦች ውህደትና ትስስር መሠረት ሆኖት የመልክዓ ምድር መገኛው ለግብርና እና ለውጭ ንግድ የተመቸ በመሆኑ በኢትዮጵያ አገረ መንግሥት ግንባታ ታሪክ ውስጥ ቁልፍ ቦታ ይዞ መኖሩን ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቃለ ምልልሳቸው መግቢያ አስታውሰውናል፡፡ ሸዋና አካባቢው ከመንግሥታት ምስረታ ጋር በተገናኘ ከዘጠነኛው አንስቶ እስካሁን ያለው ረዥም የታሪክ ጉዞ በርግጥም ሊነገር፣ ሊተነተን የአደባባይ ትርክት አካል ሊደረግ የሚገባው እውነት ነው፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከሸዋ ሡልጣኔት ምስረታ( እ.አ..አ.896 ዓ.ም.) እስከ ዓድዋ ድል(1888 ዓ.ም.) ሥላወሷቸው የአርጎባ(የወላስማ/ወሊ አስማ ሥርወ መንግሥት)፣ የአማራ(ሰለሞናዊ ሥርወ መንግሥት)፣ ኦሮሞ(ቱለማው በተለይ)፣ወርጂ፣ ጉራጌ፣ ጋፋት፣ ወዘተ ሕዝቦች ትስስርም ይሁን የፖለቲካ ጋብቻ የተመለከተ ታሪክ ከበቂ በላይ የታሪክ ማስረጃ ምንጮች ቢኖሩንም በታሪክ ግርዶሹ ምክንያት የወል ትርክት አካል መሆን አልቻለም፡፡
ኤንሪኮ ቼሩሊ ከሐረር አግኝቶ ያሳተመው በአረብኛ የተጻፈው የሸዋ ሡልጣኔት ዜና መዋዕል እንደሚያመለክተው ሡልጣኔቱን እ.አ.አ. በ896/7 የመሰረቱት የማህዙሚ ጎሳ አባላት ናቸው፡፡ መንግሥታቸውም ከ9ኛው እስከ 13ኛው ክፍለ ዘመን ድረስ በተከታታይ በገዙ አሥራ አራት ሱልጣኖች እንደጸና የታሪክ መረጃ ምንጮች ያመለክታሉ፡፡ የሸዋ ሙስሊም ሡልጣኔቱ መቀመጫ ከተማ ከአዲስ አበባ በስተሰሜን ምሥራቅ 70 ኪሎ ሜትር ላይ የምትገኝ ወለላ የተባለች ሥፍራ እንደነበረች የጆርጅ ደብሊው ቢ ሀንቲንግፎርድ(1989) ጥናት ያመለክታል፡፡ የማህዙሚ ሥርወ መንግሥት ከመጨረሻዎቹ መሪዎች አንዱ የነበረው ሡልጣን ድልመራህ ወርጂዎች የይኖሩበት በነበረው አካባቢ በ1270ዎቹ በነበረ የርስ በርስ ጦርነት ድል ሳይቀናው ሲቀር ሕይወቱን ለማትረፍ ዐጼ(የአማራ ገዥ?) እንደሄደ ይህው የአረብኛ ዜና መዋእል ያስረዳል፡፡ የማህዙሚዎች የሸዋ ሡልጣኔት የተተካው በዋናነት የአርጎባዎች አገር በሆነው ይፋት(ዊፋት) ላይ በወላስማዎች ነበር፡፡ ወላስማዎች ከአጎራባቾቻው ጋር እየተጋቡ፣ እየተስማሙም እየተጋጩም የይፋት ሡልጣኔትን ከ13ኛው እስከ 15ኛው ክፍለ ዘመን ከሸዋ እስከ ምሥራቃዊ የኢትዮጵያ ጠረፍ እንዳስተዳደሩ ስፍር ቁጥር የሌለው የሰነድ( የኢብን ካልዱን ተማሪ የነበረው አል ማቅሪዚ ጽሑፍ- ኪታብ አል ኢልማም)፣ የአርኪዮሎጂና የቃል መረጃ ምንጮች አሉ፡፡
መነሻውን ሰሜን ሸዋ እና ደቡብ ወሎ ያደረገው የክርስቲያኑ ሰሎሞናዊ ሥርወ መንግሥት በአካባቢው ያሉ ሕዝቦች ተዋህደው ከ13ኛው ክፍለ ዘመን ጀምሮ በጋራ የመሠረቱት እንደሆነ አያጠያይቅም፡፡ አማራዎች፤ አርጎባዎች፣ ወርጂዎች፣ ጋፋቶች፣ ጉራጌዎች እና ኦሮሞዎች፣ አፋሮች፣ ሐረሪዎች ወዘተ በዚህ የሸዋ መንግሥታት የተጽዕኖ ምህዳር(Orbit) ውስጥ እንደሚገኙ ዜና መዋእሎች፣ የሃይማኖት ሰነዶች፣ የአርኪዮሎጂ ማስረጃዎች ከትውልድ ወደ ትውልድ ሲተላለፉ የኖሩ የቃል መረጃ ምንጮች ያመለክታሉ፡፡ ለምሳሌ ታደሠ ታምራት(ፕሮፌሠር) ከ13ኛው እስከ 16ኛው ክፍለ ዘመን የቤተ ክርስቲያንና መንግሥትን ግንኙነት ታሪክ ባጠኑበት መጽሐፋቸው የገላንና ያያ ሰዎች ሸዋ ውስጥ በ13ኛው ክፍለ ዘመን በኦዳ ዛፍ (ኮቢል የሚባል ዋርካ) ሥር ሃይማኖታዊ ሥርዓት ይፈጽሙ እንደነበር ገድለ አቡነ ቀውስጦስን ጠቅሰው ጽፈዋል(ገጽ 184)፡፡ ሸዋ የባለ ብዙ ማንነት ሕዝቦች ሀገር ከመሆኗ ባሻገር በ16ኛው ክፍለ ዘመን የተከናወኑ ዐበይት ጉዳዮች ላይ መረጃ የተወልን መነኩሴው አባ ባህሪይ እንደገለጸው “ሸዋ የመንግሥት ሀገር ነች” (ገጽ 130)፡፡ በየዘመናቱ ከሸዋ የተነሱ የፖለቲካ ኃይሎች፣ ፈረሰኛ ሠራዊታቸውን ይዘው በሰሜን እስከ ኤርትራ(በዐጼ ሠርጸ ድንግል ዘመን- የኤርትራዋ ባሬንቱ የዚህ የታሪክ ሂደት ውርስ አይደለችም ማለት አይቻልም፡፡) በምሥራቅ እስከ ዘይላ(ከዐጼ አምደጽዮን እስከ ገላውዲዮስ ዘመን)፣ በምዕራብ እስከ ሱዳን ፋዞግሊ(ዐጼ ሱስንዮስ ዘመን) በደቡብ እስከ ሞያሌ ተንቀሳቅሰው በአገረ መንግሥት ግንባታ ሂደት ውስጥ ቁልፍ ሚና ተጫተዋል፡፡
እነዚህ የሸዋ እና አካባቢው ሕዝቦችና ገዢዎች ትልቁን ንቅናቄያቸውን ያደረጉት ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን እንደሆነ ይታወቃል፡፡ ዐጼ ምኒልክና ራስ ጎበና ዳጬ የቱለማ ኦሮሞ፤ የሸዋ አማራ እና የሌሎችም ውህድ የሆነ ጦራቸውን አዝምተው ወሎ ወግተው ወረኢሉን የመንሥታቸው መቀመጫ ያደረጉት አርሲ፣ወለጋ፣ከሐረር ከመዝመታቸው በፊት ነበር፡፡ የመጫ ኦሮሞ ተወላጁን የጎጃሙን ንጉስ ተክለሃይማኖት(አዳል ተሰማ) በቱለማው መሪ ራስ ጎበና ዳጪ እምባቦ ላይ ያስገበሩት የጂኦ ፖለቲካዊ እና የሕዝቦች ትስስር እድሎች ጉልበት ፈጥሮላቸው፤ ኃይል አጎናጽፏቸው እንጂ በአጋጣሚ አይደለም፡፡ በርግጥ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የፖለቲካችን ደንቃራነት የፈጠረውን የታሪክ ግርዶሽ ያሸነፉ ፋና ወጊ ጥናቾች መውጣት ጀምረዋል፡፡ አንዱ “Invisible Actors: The Oromo and the Creation of Modern Ethiopia(1855-1913)” በሚል ርዕስ በብሪያን ጀምስ ዬትስ(2002) በኤሊኖይስ ዩኒቨርሲቲ ከተጠናው እጅግ ጠቃሚ የዶክትሬት ዲግሪ ማሟያ ጥናት ሲሆን ሌላው የደቻሳ አበበ(ዶ/ር) ጎበና ወታደራዊና ፖለቲካዊ ሕይወት ነው፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቃለ ምልልሳቸው የዘመናዊት ኢትዮጵያን እውን መሆን ያለ ምኒልክና ያለ ጎበና እንደማይታሰብ ሲጠቅሱ ይህንን እውነታ ማጉላታቸው ይመስለኛል፡፡
የሕዝቦች ትስስርና የፖለቲካ ጋብቻ በአማራና በኦሮሞ ሕዝብ መስተጋብር ብቻ የታጠረ አልነበረም-ሊሆንም አይችልም፡፡ የኢትዮጵያ ሕዝብ ባህልና ሥልጣኔ መጋመዱ ረቂቅ ነው፡፡ ከጥንታዊ አክሱም ዘመን ጀምሮ በዝነኞቹ የአክሱም መቃብር ሀውልቶች እና በላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናት ላይ ከምናገኛቸው የኪነ ሕንጻ ትእምርቶች(Symbols) መካከል የውሸት በሮች (False Doors) እና የውሸት መስኮቶች(False windows) የሙታን መንፈስ(ኤከራ) መመላለሻ እንደሆኑ በጥናት የተረጋገጠ ነው (ቢትራይስ ፕሌይን Annales d'Éthiopie 1965) ፡፡ ይህ የኤከራዎች መመላለስና የመነጋገር ባህል እና እምነት ከደቡባዊ ግብጽ አንስቶ እስከ ሰሜን ኬንያ ድረስ በሚኖሩ የኩሽ ሕዝቦች በሰፊው የሚታወቅ ረዥም ዘመን ያስቆጠረ ልምምድ ነው፡፡
ሌላው በልኩ ያልተጠና እና በትርክቶቻችን ውስጥ ትኩረት ያልተሰጠው በሕዝቦች መካከል ያለ ሥልጣኔ ትስስር ታሪክ የእያንዳዱን የዛግዌ ነገሥታት የሥልጣን ዘመናትን የተመለከተ ነው፡፡ ከታሪክ ነገሥት፣ ከልዩ ልዩ ዜና መዋዕሎች፣ ከፖርቱጋል ተጓዦች(ፓኤዝና አልሜዳ) ከብሪቲሽ ሙዝየም እንዲሁም ከኮንቲ ሮሲኒ የተገኙት ምንጮች የሚረጋግጡት የሁሉም የዛግዌ ዐጼዎች( ከአንድ ሁለቱ በስተቀር) የሥልጣን ዘመን 40፤40 ዓመታት ነበር፡፡ ይህ ጉዳይ በኦሮሞ የገዳ ሥርዓት የአንድ ትውልድ የሥልጣን ዑደት ጋር አንድ አይነት የሆነው በአጋጣሚ ነው ወይስ ዛግዌዎች እና ኦሮሞዎች የኩሽ ሕዝቦች በመሆናቸው ቀዳሚ ከሆነው የጋራ ሥልጣኔያቸው የሚቀዳ የአስተዳደር ሥርዓት ነው? እነዚህስ ሀቆች የወል ትርክቶቻችን መመሆን አለመቻላቸው በፖለቲካ ደንቃራነት የተፈጠረ የታሪክ ግርዶሽ(eclipse of history) እንጂ ሌላ ምን ሊባል ይችላል? በላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትና እና በሸዋ በሚገኘው የአዳዲ ማርያም ቤተ ክርስቲያን ኪነሕንጻ መካከል ያለው ፍጹም ተመሳሳይነት ምንጩ ምንድነው? ሊጠና፣ ሊነገር ልንማርበት ይገባል፡፡
በርግጥም ታሪካችን ትዝታችን ላይ የተጫነ ሸክም ሳይሆን የነፍስ መገለጥ ነው የሚያሰኘው የሕዝቦች ትሥሥር፣ ውህደት የሥልጣኔ መጋራትና መወራረስ ታሪክ መታወቁ መንፈስን ሃርነት ማውጣቱ ይመስለኛል፡፡
ጋዜጠኛ ዮናስ አየለ እንደጻፈው
ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ ከአሚኮ ጋር ያደረጉትን ቃለምልልስ አዳምጬ እንደጨረስኩ በቃለ ምልልሱ በርዕሰ ጉዳይ ደረጃ ጎልተው ከወጡ ዋና ዋና ጭብጦች መካከል አንዱ ነገረ ታሪክ እንደሆነ ተሰምቶኛል፡፡ ታሪክ-የሀገር ውስጥና የውጭ፤ የሩቅና የቅርብ ዘመን! ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቃለ ምልልሳቸው ያንጸባረቁትን ሚዛናዊና አምክኖአዊ የታሪክ እይታና ድምዳሜያቸውን አለማድነቅ ንፉግነት ነው፡፡ የአሥራ ዘጠነኛው ክፍለ ዘመን እንግሊዛዊ የታሪክ ጸሐፊና ፖለቲከኛ ሎርድ አክተን “History is not a burden on the memory but an illumination of the soul” ብሎ ሲጽፍ “ታሪክ የነፍስ መገለጥ እንጂ በትዝታ ላይ የተጫነ ሸክም አይደለም” ማለቱ ነበር፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቃለ ምልልሳቸው ያነሷቸው የታሪክ አንኳር ጉዳዮች እስከዛሬ ድረስ በሀገራችን የታሪክ አጻጻፍ(Historiography) እና በሕዝባዊ ትርክቶቻችን(በሚዲያዎችን ጭምር) በሚገባቸው ልክ ያልተወሱ፤ ቢወሱም ፈራ ተባ እየተባሉ የሚጠቀሱ፤ አለፍሲልም ባልተገባ የፖለቲካ እይታ ደንቃራ ተደርገው የተወሰዱ የታሪክ ግርዶሽ(eclipse of the history) ሆነው የኖሩ ስብራቶቻችን ነበሩ፡፡ ከነዚህ ቁልፍ ጉዳዮች መካከል ዋነኛዎቹ አንዱ የሕዝቦች ትስስር እና መስተጋብር ታሪክ ሲሆን ሌላኛው በአገረ መንግስት ምሥረታ ውስጥ የሸዋ ጂኦ-ስትራቴጂካዊ ሚናን የተመለከቱት ናቸው፡፡
በመጀመሪያ የአማራና የኦሮሞ ሕዝቦች በኩታ ገጠም ቀዬዎቻቸው እና የታሪክ እድል በፈጠረላቸው የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚና የባህል አጋጣሚዎች እንደሌሎች ማህበረሰቦች ሁሉ መጋባት መዋለዳቸው፤መተሳሰር መዋሀዳቸው ሀቅ የመሆኑን ያህል የታሪክ ጥናት እና የትርክቶቻችን ማጠንጠኛ አለመሆናቸው ይታወቃል፡፡ ከዚህ በባሰ ሁኔታ ደግሞ በነገሥታቱ መካከል የነበረው የፖለቲካ ጋብቻና የመሪዎቻችን ማህበራዊ መሠረት ጉዳይ ነውር እስኪመስል በእውነታው ልክ ሳይጠናና፣ሳይነገርለት ዘመናት አልፈዋል ፡፡ በሌላ በኩል በሸዋና አካባቢው ለረዥም ዘመን የኖሩ ሕዝቦች በአገረ መንግሥት ግንባታ ሂደት የተጫወቱት ሚናና የሚጋሩት ቀደምት የሥልጣኔ ባለቤትነት (ታሪክ ሰሪነት-Agency) ግጥምጥሞሽ በሀገር መሪ ደረጃ መወሳታቸው እጅግ ጉልህ ፋይዳ ያለው ጉዳይ ነው ፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቃለ ምልልሳቸው ያነሷቸው የታሪክ እውነታዎች ያለጥርጥር ታሪካችንንና የታሪክ ምልከታችንን ደጋግመን መመርምር እንዳለብን የሚያስገነዝቡና የወገንተኝነት ጥያቄ በሚነሳባቸው ሃይማኖታዊ የታሪክ ምንጮች እንኳን የተቀመጡ ገሃድ እውነታዎች ናቸው፡፡ መመርመር ለሚፈልግ አጥኚ እነዚህ የታሪክ እውነታዎች በየነገሥታቱ ዜና መዋዕሎች (የዐጼ አምደ ጽዮን፣ ዐጼ ሱስንዮስ፣የዐጼ ገላውዲዮስ፣ የዐጼ ሠርጸ ድንግል ወዘተ)፤ የሃይማኖት ሰነዶች፣ የታሪከ ነገሥት ቅጂዎች፣ ወደ ኢትዮጵያ መጥተው የነበሩ አውሮፓውያን ተጓዦችና ጸሐፊያን (ፍራንስስኮ አልቫሬዝ፣ ፔድሮ ፔዝ፣ ማኑኤል አልሜዳ፣ ጄሮኒሞ ሎቦ፣ ጀምስ ብሩስ፣ ኮንቲ ሮሲኒ ወዘተ ) መዝግበው በተውልን ሰነዶች ሰፍረው የምናገኛቸው፤ ከትውልድ ወደ ትውልድ ሲተላለፉ የኖሩ ቱባ መረጃዎች ናቸው፡፡
ፍራንሲስኮ አልቫሬዝ የተወልን የጽሑፍ ሰነድና ሌሎች ሀገርኛ የቃል መረጃ ምንጮች ዐፄ ልብነድንግል(1498-1532 ዓ.ም.) እንደ መሪ የአማራና የኦሮሞ ብቻ ሳይሆን ምናልባትም የሌሎች ሕዝቦችም ማህበራዊ ዳራ የነበራቸው ንጉሠ ነገሥት እንደሆኑ የሚያስረዱ ሲሆን አልቫሬዝ የንጉሱ የእናት ወንድም የነበሩት አጎታቸው ዶሪ ባህረ ነጋሽ ኦሮሞ እንደነበሩና ባህረ ነጋሽ ዶሪ ሲሞቱ ሥልጣኑ በቀጥታ ወደልጃቸው ቡሎ መሸጋገሩን ጭምር በአይኑ ያየውን ጽፏል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ በትኩረት መታየት የሚገባው ጉዳይ ስለዐጼ ልብነ ድንግል የጦር አዛዦች የተነገሩ የቃል መረጃዎች ናቸወ፡፡ ከእነዚህ መካከል የንጉሠ ነገሥቱ ሠራዊት የቦረንትቻ ባሕል ያውቅ እንደነበር በተክለጻዲቅ መኩሪያ መጻፉና ከዐጼ ልብነድንግል የጦር አዛዦች አንዱ የነበረው ቱሉ ደገልሀን በመራው ከኢማም አሕመድ ጋር የተካሄደ ጦርነት የዐጼው ጦር ሲያፈገፍግ ንጉሠ ነገሥቱ “ሁሉም ቢፈራ ቱሉ እንዴት ፈራ? ” ማለታቸው ስለሠራዊታቸው ሥብጥር የሚነግረን ነገር አለ፡፡
ኦቶማን ቱርኮችን እና የዘመኑ ተላላኪዎቻቸውን ለመዋጋት የንጉሠ ነገሥቱ ሠራዊት አንድ አካል ሆነው እስከ ኤርትራ ድረስ ዘምተው ስለነበሩ የኦሮሞ ተዋጊዎች ተጋድሎ የዐጼ ሠርጸድንግል(1542-1590 ዓ.ም.) ዜና መዋእል በግልጽ አስፍሯል፡፡ እነዚህ የኦሮሞና የሌሎች ሕዝቦች ተወላጅ ወታደሮች ትግራይ እንጢጮ አካባቢ ያካሄዱትን አውደ ውጊያ ዜና መዋዕሉ ይተርካል፡፡ ለመንግሥታቸውና ለሀገራቸው እስከባሕር ጠረፍ ድረስ ዘምተው ዋጋ መክፈላቸውም ተመዝግቧል፡፡ የዐጼ ሱስንዮስ(1607-1632 ዓ.ም.) ዜና መዋእል እና በዘመኑ ኢትዮጵያ መጥተው የነበሩ የአውሮፓ(የፖርቱጋል) ተጓዦች የጻፏቸው የመረጃ ምንጮች ንጉሠ ነገሥቱ ግንደበረት፣ሐምቦና አካባቢው ቤታቸው እንደነበር፤ አጎታቸው ለማሞ እንደሚባል፣ ወላጅ እናታቸው(ሐመልማል ወርቅ) የአዛዥ ኩሎ ልጅ የነበረች፤ የዚሁ የሐመልማል ወርቅ ጎሳ ተወላጅ የሆነ ቡኮ የተባለ ኦሮሞና ሠራዊቱ ለአባይ ቅርብ የሆነች ምዕራብ ሸዋ ላይ ዐጼ ሱስንዮስ ሲያገኙት የነበረውን ደስታና የፍቅሩን ጽናት ዜና መዋዕሉ ሳይሰስት ጽፎታል፡፡ ዐጼ ፋሲል(ከ1632 እስከ 1667 ዓ.ም.) አባቱ ሱስንዮስ እናቱ የወሎ ቃሉ ሰው(እቴጌ ሥልጣን ሞገሳ የሚል ስም የተሰጣት) እንደሆነች የታሪክ ምንጮች ያስረዱናል፡፡ በ1620ዎቹ ዓመታት ጀምሮ በኢትዮጵያ ይኖር የነበረው ፖርቱጋላዊ ቄስ ጄሮኒሞ ሎቦ ስለዐጼ ፋሲል እናትና ኦሮሞ ዘመዶቻቸው በአይን ምስክርነት የሚያውቀውን ጽፏል፡፡ የእቴጌ ሥልጣን ሞገሳ አያት ስለብዝሀ ሃይማኖት አስፈላጊነት የነበራቸውን ግልጽ ፖሊሲ ጭምር ሎቦ ዘግቦታል፡፡ የዐጼ በካፋ(1721-1730 ዓ.ም.) እና የዐጼ ኢዮአስ(1747-1761 ዓ.ም.) ጎንደር መቼም ለሕዝቦች ውህደትና ትስስር ጥሩ ማሳያ ነበረች፡፡ የየጁ ኦሮሞ ገዢ የነበረው የአሚቶ ሴት ልጅ ዝነኛዋ ውቢት ልጇ ዐጼ አዮአስ ነበር፡፡ ኢዮአስ ከኦሮሞ አጎቱ ከደጃች ሉቦ ጋር ሥልጣኑን በጎንደር እንዴት እንዳጸና፤ የቤተ መንግሥቱም የሥራ ቋንቋ አፋን ኦሮሞ እንደነበረ የንጉሠ ነገሥቱ ዜና መዋዕልና በጀምስ ብሩስ ቅጽ ሁለት መጽሀፍ የተመዘገቡ የታሪክ መረጃዎች ያስረዱናል፡፡
መነሻውን ወሎ በማድረግ ጎንደር ጸንቶ የኖረው የየጁ ሥርወ መንግሥት(ወረ ሼኮች) መሥራቾች የመርሳው አባ ጌትዬ፣ የልጃቸው ጓንጉል አባ ሴሩ እንዲሁም የልጅ ልጃቸው የራስ አሊ ጓንጉል(አሊ ትልቁ) ታሪክ በኢዮአስ ዜና መዋዕል፣ በጀምስ ብሩስ መጽሐፍና በሌሎች በርካታ ሰነዶች ታሪካቸው ተዘግቧል፡፡ በኋላ ላይ በሽፈራው በቀለ(ፕሮፌሰር) እና ሞላ ትኩዬ የቀረቡ ጥልቅ ጥናቶች ይህን እውነት በዝርዝር ያስረዱናል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቃለ ምልልሳቸው እንደጠቀሱት የእነዚህ መሪዎች የፖለቲካ ጋብቻ ታሪክ የሚያሳየን በሄዱበት አገር ሁሉ የሕዝቦች ትሥሥር እና የፖለቲካ ጋብቻ የኖረ ታሪካችን እና የጉልበታችን ምንጭ እንደነበረ ነው፡፡ በዳግማዊ ዐጼ ቴዎድሮስ ዘመን የተጻፉ የታሪክ ሰነዶች የወሎዋ ገዢ ወርቂቱ ወዳጆ(የማመዶች ሥርወ መንግሥት መሪ የኢማም አሊ አባ ቡላ ባለቤት) ንጉሥ ምኒልክ ከመቅደላ እስር ቤት እንዲያመልጡ ያደረጉ፤ አጃቢ ሠራዊት አሰማርተው ምኒልክን እስከሸዋ የሸኙ እንደነበሩ በዋናነት ከጸሓፌ ትእዛዝ ገብረ ሥላሴ ታሪከ ዘመን ዘ ዳግማዊ ምኒልክ ዜና መዋዕል እና በመቅደላ አምባ እስር ላይ የነበሩ አውሮፓውያን ከጻፏቸው መረጃዎች እንረዳለን፡፡
ሥልጣኔዎቻችን ሁሉ ተደምረን ያሳካናቸው እንደሆነ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቃለ ምልልሳቸው አንስተዋል፡፡ የዐድዋ ዘመቻና ድሉ ለዚህ አንዱ ማሳያ እንደሆነ ተጨባጭ የታሪክ ምንጮች ያስረዱናል፡፡ በ1888 ዓ.ም. ለዓድዋ ዘመቻ ከመላው ኢትዮጵያ የተመመው ሠረዊት ወፍላ ላይ የነበረው ሠልፍ የንጉሠ ነገሥቱ ዜና መዋዕል እንኳን እንዲህ ይገልጸዋል፡፡ “የመኳንንቱ የጦር መሣሪያ፣ወርቁ፣ ጣፋ፣ ብሩ፣ ሙጣው፣ ጫሜው፣ ሎሚታውና ኩፊታው፣ ከሌቻው፣ ወርቅ ለምዱ እንደጸሐይ ሲያበራ ዋለ፡፡” እንደጸሐይ የበራውን ሕብረ ባሕልና ሕብረ ማንነት ትርክቶቻችን በልኩ አጉልተው ያውቃሉ?
ሸዋና አካባቢው(ወሎን ጨምሮ) እንደ አንድ ጂዞ ስትራቴጂ ሥፍራ የሕዝቦች ውህደትና ትስስር መሠረት ሆኖት የመልክዓ ምድር መገኛው ለግብርና እና ለውጭ ንግድ የተመቸ በመሆኑ በኢትዮጵያ አገረ መንግሥት ግንባታ ታሪክ ውስጥ ቁልፍ ቦታ ይዞ መኖሩን ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቃለ ምልልሳቸው መግቢያ አስታውሰውናል፡፡ ሸዋና አካባቢው ከመንግሥታት ምስረታ ጋር በተገናኘ ከዘጠነኛው አንስቶ እስካሁን ያለው ረዥም የታሪክ ጉዞ በርግጥም ሊነገር፣ ሊተነተን የአደባባይ ትርክት አካል ሊደረግ የሚገባው እውነት ነው፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከሸዋ ሡልጣኔት ምስረታ( እ.አ..አ.896 ዓ.ም.) እስከ ዓድዋ ድል(1888 ዓ.ም.) ሥላወሷቸው የአርጎባ(የወላስማ/ወሊ አስማ ሥርወ መንግሥት)፣ የአማራ(ሰለሞናዊ ሥርወ መንግሥት)፣ ኦሮሞ(ቱለማው በተለይ)፣ወርጂ፣ ጉራጌ፣ ጋፋት፣ ወዘተ ሕዝቦች ትስስርም ይሁን የፖለቲካ ጋብቻ የተመለከተ ታሪክ ከበቂ በላይ የታሪክ ማስረጃ ምንጮች ቢኖሩንም በታሪክ ግርዶሹ ምክንያት የወል ትርክት አካል መሆን አልቻለም፡፡
ኤንሪኮ ቼሩሊ ከሐረር አግኝቶ ያሳተመው በአረብኛ የተጻፈው የሸዋ ሡልጣኔት ዜና መዋዕል እንደሚያመለክተው ሡልጣኔቱን እ.አ.አ. በ896/7 የመሰረቱት የማህዙሚ ጎሳ አባላት ናቸው፡፡ መንግሥታቸውም ከ9ኛው እስከ 13ኛው ክፍለ ዘመን ድረስ በተከታታይ በገዙ አሥራ አራት ሱልጣኖች እንደጸና የታሪክ መረጃ ምንጮች ያመለክታሉ፡፡ የሸዋ ሙስሊም ሡልጣኔቱ መቀመጫ ከተማ ከአዲስ አበባ በስተሰሜን ምሥራቅ 70 ኪሎ ሜትር ላይ የምትገኝ ወለላ የተባለች ሥፍራ እንደነበረች የጆርጅ ደብሊው ቢ ሀንቲንግፎርድ(1989) ጥናት ያመለክታል፡፡ የማህዙሚ ሥርወ መንግሥት ከመጨረሻዎቹ መሪዎች አንዱ የነበረው ሡልጣን ድልመራህ ወርጂዎች የይኖሩበት በነበረው አካባቢ በ1270ዎቹ በነበረ የርስ በርስ ጦርነት ድል ሳይቀናው ሲቀር ሕይወቱን ለማትረፍ ዐጼ(የአማራ ገዥ?) እንደሄደ ይህው የአረብኛ ዜና መዋእል ያስረዳል፡፡ የማህዙሚዎች የሸዋ ሡልጣኔት የተተካው በዋናነት የአርጎባዎች አገር በሆነው ይፋት(ዊፋት) ላይ በወላስማዎች ነበር፡፡ ወላስማዎች ከአጎራባቾቻው ጋር እየተጋቡ፣ እየተስማሙም እየተጋጩም የይፋት ሡልጣኔትን ከ13ኛው እስከ 15ኛው ክፍለ ዘመን ከሸዋ እስከ ምሥራቃዊ የኢትዮጵያ ጠረፍ እንዳስተዳደሩ ስፍር ቁጥር የሌለው የሰነድ( የኢብን ካልዱን ተማሪ የነበረው አል ማቅሪዚ ጽሑፍ- ኪታብ አል ኢልማም)፣ የአርኪዮሎጂና የቃል መረጃ ምንጮች አሉ፡፡
መነሻውን ሰሜን ሸዋ እና ደቡብ ወሎ ያደረገው የክርስቲያኑ ሰሎሞናዊ ሥርወ መንግሥት በአካባቢው ያሉ ሕዝቦች ተዋህደው ከ13ኛው ክፍለ ዘመን ጀምሮ በጋራ የመሠረቱት እንደሆነ አያጠያይቅም፡፡ አማራዎች፤ አርጎባዎች፣ ወርጂዎች፣ ጋፋቶች፣ ጉራጌዎች እና ኦሮሞዎች፣ አፋሮች፣ ሐረሪዎች ወዘተ በዚህ የሸዋ መንግሥታት የተጽዕኖ ምህዳር(Orbit) ውስጥ እንደሚገኙ ዜና መዋእሎች፣ የሃይማኖት ሰነዶች፣ የአርኪዮሎጂ ማስረጃዎች ከትውልድ ወደ ትውልድ ሲተላለፉ የኖሩ የቃል መረጃ ምንጮች ያመለክታሉ፡፡ ለምሳሌ ታደሠ ታምራት(ፕሮፌሠር) ከ13ኛው እስከ 16ኛው ክፍለ ዘመን የቤተ ክርስቲያንና መንግሥትን ግንኙነት ታሪክ ባጠኑበት መጽሐፋቸው የገላንና ያያ ሰዎች ሸዋ ውስጥ በ13ኛው ክፍለ ዘመን በኦዳ ዛፍ (ኮቢል የሚባል ዋርካ) ሥር ሃይማኖታዊ ሥርዓት ይፈጽሙ እንደነበር ገድለ አቡነ ቀውስጦስን ጠቅሰው ጽፈዋል(ገጽ 184)፡፡ ሸዋ የባለ ብዙ ማንነት ሕዝቦች ሀገር ከመሆኗ ባሻገር በ16ኛው ክፍለ ዘመን የተከናወኑ ዐበይት ጉዳዮች ላይ መረጃ የተወልን መነኩሴው አባ ባህሪይ እንደገለጸው “ሸዋ የመንግሥት ሀገር ነች” (ገጽ 130)፡፡ በየዘመናቱ ከሸዋ የተነሱ የፖለቲካ ኃይሎች፣ ፈረሰኛ ሠራዊታቸውን ይዘው በሰሜን እስከ ኤርትራ(በዐጼ ሠርጸ ድንግል ዘመን- የኤርትራዋ ባሬንቱ የዚህ የታሪክ ሂደት ውርስ አይደለችም ማለት አይቻልም፡፡) በምሥራቅ እስከ ዘይላ(ከዐጼ አምደጽዮን እስከ ገላውዲዮስ ዘመን)፣ በምዕራብ እስከ ሱዳን ፋዞግሊ(ዐጼ ሱስንዮስ ዘመን) በደቡብ እስከ ሞያሌ ተንቀሳቅሰው በአገረ መንግሥት ግንባታ ሂደት ውስጥ ቁልፍ ሚና ተጫተዋል፡፡
እነዚህ የሸዋ እና አካባቢው ሕዝቦችና ገዢዎች ትልቁን ንቅናቄያቸውን ያደረጉት ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን እንደሆነ ይታወቃል፡፡ ዐጼ ምኒልክና ራስ ጎበና ዳጬ የቱለማ ኦሮሞ፤ የሸዋ አማራ እና የሌሎችም ውህድ የሆነ ጦራቸውን አዝምተው ወሎ ወግተው ወረኢሉን የመንሥታቸው መቀመጫ ያደረጉት አርሲ፣ወለጋ፣ከሐረር ከመዝመታቸው በፊት ነበር፡፡ የመጫ ኦሮሞ ተወላጁን የጎጃሙን ንጉስ ተክለሃይማኖት(አዳል ተሰማ) በቱለማው መሪ ራስ ጎበና ዳጪ እምባቦ ላይ ያስገበሩት የጂኦ ፖለቲካዊ እና የሕዝቦች ትስስር እድሎች ጉልበት ፈጥሮላቸው፤ ኃይል አጎናጽፏቸው እንጂ በአጋጣሚ አይደለም፡፡ በርግጥ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የፖለቲካችን ደንቃራነት የፈጠረውን የታሪክ ግርዶሽ ያሸነፉ ፋና ወጊ ጥናቾች መውጣት ጀምረዋል፡፡ አንዱ “Invisible Actors: The Oromo and the Creation of Modern Ethiopia(1855-1913)” በሚል ርዕስ በብሪያን ጀምስ ዬትስ(2002) በኤሊኖይስ ዩኒቨርሲቲ ከተጠናው እጅግ ጠቃሚ የዶክትሬት ዲግሪ ማሟያ ጥናት ሲሆን ሌላው የደቻሳ አበበ(ዶ/ር) ጎበና ወታደራዊና ፖለቲካዊ ሕይወት ነው፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቃለ ምልልሳቸው የዘመናዊት ኢትዮጵያን እውን መሆን ያለ ምኒልክና ያለ ጎበና እንደማይታሰብ ሲጠቅሱ ይህንን እውነታ ማጉላታቸው ይመስለኛል፡፡
የሕዝቦች ትስስርና የፖለቲካ ጋብቻ በአማራና በኦሮሞ ሕዝብ መስተጋብር ብቻ የታጠረ አልነበረም-ሊሆንም አይችልም፡፡ የኢትዮጵያ ሕዝብ ባህልና ሥልጣኔ መጋመዱ ረቂቅ ነው፡፡ ከጥንታዊ አክሱም ዘመን ጀምሮ በዝነኞቹ የአክሱም መቃብር ሀውልቶች እና በላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናት ላይ ከምናገኛቸው የኪነ ሕንጻ ትእምርቶች(Symbols) መካከል የውሸት በሮች (False Doors) እና የውሸት መስኮቶች(False windows) የሙታን መንፈስ(ኤከራ) መመላለሻ እንደሆኑ በጥናት የተረጋገጠ ነው (ቢትራይስ ፕሌይን Annales d'Éthiopie 1965) ፡፡ ይህ የኤከራዎች መመላለስና የመነጋገር ባህል እና እምነት ከደቡባዊ ግብጽ አንስቶ እስከ ሰሜን ኬንያ ድረስ በሚኖሩ የኩሽ ሕዝቦች በሰፊው የሚታወቅ ረዥም ዘመን ያስቆጠረ ልምምድ ነው፡፡
ሌላው በልኩ ያልተጠና እና በትርክቶቻችን ውስጥ ትኩረት ያልተሰጠው በሕዝቦች መካከል ያለ ሥልጣኔ ትስስር ታሪክ የእያንዳዱን የዛግዌ ነገሥታት የሥልጣን ዘመናትን የተመለከተ ነው፡፡ ከታሪክ ነገሥት፣ ከልዩ ልዩ ዜና መዋዕሎች፣ ከፖርቱጋል ተጓዦች(ፓኤዝና አልሜዳ) ከብሪቲሽ ሙዝየም እንዲሁም ከኮንቲ ሮሲኒ የተገኙት ምንጮች የሚረጋግጡት የሁሉም የዛግዌ ዐጼዎች( ከአንድ ሁለቱ በስተቀር) የሥልጣን ዘመን 40፤40 ዓመታት ነበር፡፡ ይህ ጉዳይ በኦሮሞ የገዳ ሥርዓት የአንድ ትውልድ የሥልጣን ዑደት ጋር አንድ አይነት የሆነው በአጋጣሚ ነው ወይስ ዛግዌዎች እና ኦሮሞዎች የኩሽ ሕዝቦች በመሆናቸው ቀዳሚ ከሆነው የጋራ ሥልጣኔያቸው የሚቀዳ የአስተዳደር ሥርዓት ነው? እነዚህስ ሀቆች የወል ትርክቶቻችን መመሆን አለመቻላቸው በፖለቲካ ደንቃራነት የተፈጠረ የታሪክ ግርዶሽ(eclipse of history) እንጂ ሌላ ምን ሊባል ይችላል? በላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትና እና በሸዋ በሚገኘው የአዳዲ ማርያም ቤተ ክርስቲያን ኪነሕንጻ መካከል ያለው ፍጹም ተመሳሳይነት ምንጩ ምንድነው? ሊጠና፣ ሊነገር ልንማርበት ይገባል፡፡
በርግጥም ታሪካችን ትዝታችን ላይ የተጫነ ሸክም ሳይሆን የነፍስ መገለጥ ነው የሚያሰኘው የሕዝቦች ትሥሥር፣ ውህደት የሥልጣኔ መጋራትና መወራረስ ታሪክ መታወቁ መንፈስን ሃርነት ማውጣቱ ይመስለኛል፡፡
1 day ago
ኩባንያችን 8ኛውን ዙር የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር በይፋ አስጀመረ!
ኩባንያችን የአረንጓዴ ኦፕሬተርነት ጉዞውን በማጠናከር፣ ዛሬ በሀገር አቀፍ ደረጃ “ለአረንጓዴ ኢትዮጵያ” በሚል መሪ ቃል 250 ሺህ ችግኞችን በስኬት ተክሏል፡፡ በዚህም በአዲስ አበባ እንጦጦ (ቁስቋም ማዞሪያ) እንዲሁም በመላው ሀገሪቱ በሚገኙ ከተሞች አረንጓዴ አሻራችንን አሳርፈናል፡፡
በመርሃ-ግብሩ ላይ ዋና ሥራ አስፈጻሚያችን ፍሬሕይወት ታምሩ እንደገለጹት፤ ይህ ተግባር ኩባንያችን በዘላቂነት ስትራቴጂው (Sustainability Strategy) የሚያከናውናቸው ተግባራት አካል ሲሆን፣ ባለፉት ሰባት ዓመታት ከተተከሉ ከ4.6 ሚሊዮን በላይ ችግኞች 82.7% እንዲጸድቁ መደረጉን አብራርተዋል።
በተጨማሪም በታዳሽ የኃይል ኢንቨስትመንቶች፣ በፀሐይ ኃይል የሚሠሩ የኔትወርክ መሠረተ-ልማቶች እና ኃይል ቆጣቢ አረንጓዴ የዳታ ማዕከላት አማካኝነት የካርቦን ልቀት ቅነሳን ማሳካት ተችሏል። በተመሳሳይ በገነባናቸው ከ9 በላይ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ መሙያ ጣቢያዎች ከ481 ሺህ በላይ ተሽከርካሪዎችን በማስተናገድ፣ ከ15.4 ሚሊዮን ኪሎግራም በላይ የካርቦን ልቀትን መከላከል ተችሏል፤ ይህም ከ76 ሺህ በላይ ዛፎችን ከመትከል ጋር እኩል ፋይዳ አለው።
የጉለሌ ክፍለ ከተማ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ወልዴ ወገሴ በመርሃ-ግብሩ ባስተላለፉት መልዕክት፤ ኢትዮ ቴሌኮም ችግኝ መትከል ብቻ ሳይሆን ለመንከባከብ ትኩረት የሚሰጥ ተቋም መሆኑን ገልጸው፣ ከዚህ ቀደም የተተከሉ ችግኞች ወደ ጫካነት መቀየራቸውን በመጥቀስ ልባዊ ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡
በ8ኛው ዙር መርሃ-ግብር ለተከላና እንክብካቤ ሥራዎች ከ2,000 በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የሥራ ዕድል የሚፈጠር ሲሆን፣ ባለፉት ሰባት ዓመታት ውስጥ በአጠቃላይ ከ24.8 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠር ተችሏል፡፡
በዚህ የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር ላይ በንቃት ለተሳተፋችሁ የኩባንያችን ቤተሰቦች፣ አጋሮቻችን እና የመትከያ ቦታ ላመቻቻችሁ የመንግስት አካላት ምስጋና እናቀርባለን፡፡
ለበለጠ፡ https://bit.ly/4xhlXxF
#digitalethiopia #digitalafrica #gsma #itu #worldbank #oecd #g6countries
ኩባንያችን የአረንጓዴ ኦፕሬተርነት ጉዞውን በማጠናከር፣ ዛሬ በሀገር አቀፍ ደረጃ “ለአረንጓዴ ኢትዮጵያ” በሚል መሪ ቃል 250 ሺህ ችግኞችን በስኬት ተክሏል፡፡ በዚህም በአዲስ አበባ እንጦጦ (ቁስቋም ማዞሪያ) እንዲሁም በመላው ሀገሪቱ በሚገኙ ከተሞች አረንጓዴ አሻራችንን አሳርፈናል፡፡
በመርሃ-ግብሩ ላይ ዋና ሥራ አስፈጻሚያችን ፍሬሕይወት ታምሩ እንደገለጹት፤ ይህ ተግባር ኩባንያችን በዘላቂነት ስትራቴጂው (Sustainability Strategy) የሚያከናውናቸው ተግባራት አካል ሲሆን፣ ባለፉት ሰባት ዓመታት ከተተከሉ ከ4.6 ሚሊዮን በላይ ችግኞች 82.7% እንዲጸድቁ መደረጉን አብራርተዋል።
በተጨማሪም በታዳሽ የኃይል ኢንቨስትመንቶች፣ በፀሐይ ኃይል የሚሠሩ የኔትወርክ መሠረተ-ልማቶች እና ኃይል ቆጣቢ አረንጓዴ የዳታ ማዕከላት አማካኝነት የካርቦን ልቀት ቅነሳን ማሳካት ተችሏል። በተመሳሳይ በገነባናቸው ከ9 በላይ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ መሙያ ጣቢያዎች ከ481 ሺህ በላይ ተሽከርካሪዎችን በማስተናገድ፣ ከ15.4 ሚሊዮን ኪሎግራም በላይ የካርቦን ልቀትን መከላከል ተችሏል፤ ይህም ከ76 ሺህ በላይ ዛፎችን ከመትከል ጋር እኩል ፋይዳ አለው።
የጉለሌ ክፍለ ከተማ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ወልዴ ወገሴ በመርሃ-ግብሩ ባስተላለፉት መልዕክት፤ ኢትዮ ቴሌኮም ችግኝ መትከል ብቻ ሳይሆን ለመንከባከብ ትኩረት የሚሰጥ ተቋም መሆኑን ገልጸው፣ ከዚህ ቀደም የተተከሉ ችግኞች ወደ ጫካነት መቀየራቸውን በመጥቀስ ልባዊ ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡
በ8ኛው ዙር መርሃ-ግብር ለተከላና እንክብካቤ ሥራዎች ከ2,000 በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የሥራ ዕድል የሚፈጠር ሲሆን፣ ባለፉት ሰባት ዓመታት ውስጥ በአጠቃላይ ከ24.8 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠር ተችሏል፡፡
በዚህ የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር ላይ በንቃት ለተሳተፋችሁ የኩባንያችን ቤተሰቦች፣ አጋሮቻችን እና የመትከያ ቦታ ላመቻቻችሁ የመንግስት አካላት ምስጋና እናቀርባለን፡፡
ለበለጠ፡ https://bit.ly/4xhlXxF
#digitalethiopia #digitalafrica #gsma #itu #worldbank #oecd #g6countries
2 days ago
እነሆ ''ተስፋን እንትከል'''
#ethiopia | "ዛፍ ለመትከል የተሻለው ጊዜ ከ20 ዓመታት በፊት ነበር፤ ሁለተኛው የተሻለው ጊዜ ደግሞ አሁን ነው" እንደሚባለው ሁሉ፣ ዛፍ መትከል ተስፋን መትከል በመሆኑና ሕይወታችንን ሰናይ ለማድረግ ደኖቻችንን ማልማት አስፈላጊ ነው።
በዓለም አቀፍ ደረጃ የምድራችን 31 ከመቶ የሚሆነው አካል በደን የተሸፈነ ቢሆንም፣ የደን ሽፋን በየጊዜው እያቆለቆለ በመምጣቱ እስከ እ.ኤ.አ 2030 ድረስ 1 ትሪሊዮን ዛፎችን ለመትከልና ለመንከባከብ እንቅስቃሴ እየተደረገ ይገኛል።
በሀገራችን በ20ኛው ክፍለ ዘመን መጀመሪያ ላይ 40 ከመቶ የነበረው የደን ሽፋን ለእርሻ መሬት መስፋፋት ሲባል ተመንጥሮ ወደ 2 ከመቶ ወርዶ የነበረ ቢሆንም፣ ባለፉት አምስት ዓመታት በተደረገው ከፍተኛ ጥረት የደን ሽፋኑ በ2023 ወደ 23.6 ከመቶ ማደግ ችሏል።
በዚህ መነሻም የፌዴራል ቱሪዝም ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሆሳዕና ከተማ የክረምት ወራት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት አካል የሆኑ ሀገራዊና ማህበራዊ ልማቶችን አከናውኗል።
በኢንስቲትዩቱ "ተስፋን እንተክላለን" በሚል ሀገራዊ ራዕይ የአንድ ጀንበር የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በማካሄድ ከአካባቢው ማህበረሰብ ጋር በመተባበር በቦቢቾ ቀበሌ ለምግብነትና ለአካባቢ ጥበቃ የሚውሉ 5 ሺህ ችግኞችን ተክሏል።
ከችግኝ ተከላው ጎን ለጎንም በጀሎ ናረሞ ቀበሌ "የዛሬ ህፃናት የነገ ተስፋ ናቸው" በሚል መሪ ቃል የነገ ሀገር ተረካቢ ህፃናትን አእምሯዊ እድገት ለመደገፍ የሚያስችል ዘመናዊ የመዋዕለ ህፃናት ግንባታ መሠረት ድንጋይ አኖሯል።
በዚሁ መርሃ ግብር ላይ ኢንስቲትዩቱ ከግንባታው ባሻገር ለአንድ ሺህ ተማሪዎች የሚሆን የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ ለሆሳዕና ከተማ ከንቲባ ለአቶ ሳሙኤል ሽጉጤ እና ለትምህርት ጽሕፈት ቤት ሃላፊው አስረክቧል።
የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር አቶ ጌታቸው ነጋሽ የክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ሀገራዊ አንድነትን እንደሚያጠናክር ገልጸው፣ ደረጃውን የጠበቀ እና በቴክኖሎጂ የታገዘ የትምህርት ቁሳቁስ የሚሟላለት ይህ መዋዕለ ህፃናት በአጭር ጊዜ ውስጥ ተገንብቶ ለአገልግሎት እንዲበቃ አስፈላጊው ክትትል እንደሚደረግ አረጋግጠዋል።
የሆሳዕና ከተማ ከንቲባ አቶ ሳሙኤል ሽጉጤ እና የአካባቢው የሀገር ሽማግሌዎች ለተከናወኑት የልማትና የበጎ አድራጎት ሥራዎች ለኢንስቲትዩቱ አመራሮችና ሠራተኞች ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
ለ Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን) ሚዲያና ኮሙኒኬሽን
ያፌት ገ/ህይወት
ከሀዲያ ዞን ፤ ሆሳዕና
#ethiopia | "ዛፍ ለመትከል የተሻለው ጊዜ ከ20 ዓመታት በፊት ነበር፤ ሁለተኛው የተሻለው ጊዜ ደግሞ አሁን ነው" እንደሚባለው ሁሉ፣ ዛፍ መትከል ተስፋን መትከል በመሆኑና ሕይወታችንን ሰናይ ለማድረግ ደኖቻችንን ማልማት አስፈላጊ ነው።
በዓለም አቀፍ ደረጃ የምድራችን 31 ከመቶ የሚሆነው አካል በደን የተሸፈነ ቢሆንም፣ የደን ሽፋን በየጊዜው እያቆለቆለ በመምጣቱ እስከ እ.ኤ.አ 2030 ድረስ 1 ትሪሊዮን ዛፎችን ለመትከልና ለመንከባከብ እንቅስቃሴ እየተደረገ ይገኛል።
በሀገራችን በ20ኛው ክፍለ ዘመን መጀመሪያ ላይ 40 ከመቶ የነበረው የደን ሽፋን ለእርሻ መሬት መስፋፋት ሲባል ተመንጥሮ ወደ 2 ከመቶ ወርዶ የነበረ ቢሆንም፣ ባለፉት አምስት ዓመታት በተደረገው ከፍተኛ ጥረት የደን ሽፋኑ በ2023 ወደ 23.6 ከመቶ ማደግ ችሏል።
በዚህ መነሻም የፌዴራል ቱሪዝም ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሆሳዕና ከተማ የክረምት ወራት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት አካል የሆኑ ሀገራዊና ማህበራዊ ልማቶችን አከናውኗል።
በኢንስቲትዩቱ "ተስፋን እንተክላለን" በሚል ሀገራዊ ራዕይ የአንድ ጀንበር የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በማካሄድ ከአካባቢው ማህበረሰብ ጋር በመተባበር በቦቢቾ ቀበሌ ለምግብነትና ለአካባቢ ጥበቃ የሚውሉ 5 ሺህ ችግኞችን ተክሏል።
ከችግኝ ተከላው ጎን ለጎንም በጀሎ ናረሞ ቀበሌ "የዛሬ ህፃናት የነገ ተስፋ ናቸው" በሚል መሪ ቃል የነገ ሀገር ተረካቢ ህፃናትን አእምሯዊ እድገት ለመደገፍ የሚያስችል ዘመናዊ የመዋዕለ ህፃናት ግንባታ መሠረት ድንጋይ አኖሯል።
በዚሁ መርሃ ግብር ላይ ኢንስቲትዩቱ ከግንባታው ባሻገር ለአንድ ሺህ ተማሪዎች የሚሆን የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ ለሆሳዕና ከተማ ከንቲባ ለአቶ ሳሙኤል ሽጉጤ እና ለትምህርት ጽሕፈት ቤት ሃላፊው አስረክቧል።
የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር አቶ ጌታቸው ነጋሽ የክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ሀገራዊ አንድነትን እንደሚያጠናክር ገልጸው፣ ደረጃውን የጠበቀ እና በቴክኖሎጂ የታገዘ የትምህርት ቁሳቁስ የሚሟላለት ይህ መዋዕለ ህፃናት በአጭር ጊዜ ውስጥ ተገንብቶ ለአገልግሎት እንዲበቃ አስፈላጊው ክትትል እንደሚደረግ አረጋግጠዋል።
የሆሳዕና ከተማ ከንቲባ አቶ ሳሙኤል ሽጉጤ እና የአካባቢው የሀገር ሽማግሌዎች ለተከናወኑት የልማትና የበጎ አድራጎት ሥራዎች ለኢንስቲትዩቱ አመራሮችና ሠራተኞች ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
ለ Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን) ሚዲያና ኮሙኒኬሽን
ያፌት ገ/ህይወት
ከሀዲያ ዞን ፤ ሆሳዕና
Sponsored by
Surafel
2 days ago
የጤናው ዘርፍ የአረንጓዴ አሻራ ተሳትፎ
📌 ከ30 ሺህ በላይ ችግኞች በዛሬው እለት ተተክለዋል
#ethiopia | በሀገር አቀፍ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር ላይ የጤና ሚኒስቴር እና የተጠሪ ተቋማት አመራሮች እንዲሁም ሰራተኞች ከኢትዮጵያ የአካል ድጋፍ አገልግሎት ከገፈርሳ ጉጄ ክፍለ ከተማ ጋር በመተባበር በዛሬ እለት በገፈርሳ ሰው ሰራሽ ሀይቅ ዳርቻ ከ30 ሺህ በላይ ችግኞች በዛሬው እለት ተተክለዋል።
በሸገር ከተማ በገፈርሳ ጉጄ አካባቢ በተካሄደው በዚህ የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር ላይ የጤና ሚኒስትሯ ክብርት ዶክተር መቅደስ ዳባ፣ ሚኒስትር ዴኤታዎች እና የየደረጃው የአካባቢው አመራሮች እንዲሁም የሀገር መከላከያ ሰራዊት አባላትና የማህበረሰብ ክፍሎች ከማለዳው 1 ሰዓት ጀምሮ በመገኘት ችግኝ ተክለዋል።
የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ደረጄ ዱጉማ በዚሁ ወቅት ባደረጉት ንግግር፣ አረንጓዴ አሻራ እና የጤና ዘርፍ የማይለያዩ የአንድ ሳንቲም ሁለት ገጽታዎች መሆናቸውን ገልጸዋል። ችግኝ ለአካባቢ ጥበቃ ብቻ ሳይሆን ለህብረተሰብ ጤና፣ ለንጹህ አየር እና ለምግብ ዋስትና ማሻሻያ ወሳኝ ሚና እንደሚጫወት የጠቆሙት ሚኒስትር ዴኤታው፣ በተለይም ለአዲስ አበባ እና ለአካባቢው ህዝብ የንጹህ ውሃ ምንጭ የሆነውን የገፈርሳ አካባቢን መንከባከብ የሁላችንም ህብረ-ብሄራዊ ሀገራዊ ኃላፊነት እንደሆነ አስገንዝበዋል።
በዕለቱ በቦታው ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የጤና ሚኒስትሯ ክብርት ዶክተር መቅደስ ዳባ በበኩላቸው፣ ኢትዮጵያ የተፈጥሮ አካባቢዋን ለመጠበቅ የምታደርገው ጥረት በንግግር ሳይሆን በተግባር የሚገለጽ መሆኑን አብራርተዋል።
በዕለቱ ሚኒስቴሩ ከተጠሪ ተቋማት ጋር በመሆን ከ30 ሺህ በላይ ችግኞችን የተከለ ሲሆን፣ በክረምቱ የክረምት በጎ ፈቃድ መርሃ-ግብር ደግሞ በሀገር አቀፍ ደረጃ እስከ 250 ሺህ ችግኞችን ለመትከል እና ከ20 ሚሊዮን በላይ ዜጎችን ነጻ የህክምና አገልግሎት ለመስጠት ታቅዶ እየተሰራ እንደሚገኝ ሚኒስትሯ ገልጸዋል።
በመጨረሻም ክብርት ሚኒስትሯ፣ የጤና ባለሙያዎች እና መላው የሀገራችን ህዝብ ቀኑ ሳያልቅ እና ጀምበር ሳትጠልቅ የድርሻቸውን ችግኝ በመትከል የዚህ ታሪካዊ ኩነት አካል እንዲሆኑ ጥሪ አቅርበዋል።
ከችግኝ ተከላው መርሐግብር ባሻገር የኢትዮጵያ የአካል ድጋፍ አገልግሎት በሸገር ከተማ ከ200 በላይ ለሚሆኑ ተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ ተደርጓል።
በጌትነት ተመስገን
📷 ከበደ መክብብ
#ministryofhealth #treeplanting
#climateaction #publichealth
#environmentalhealth #gefersa #cleanenvironment #greenethiopia
#communitysupport
📌 ከ30 ሺህ በላይ ችግኞች በዛሬው እለት ተተክለዋል
#ethiopia | በሀገር አቀፍ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር ላይ የጤና ሚኒስቴር እና የተጠሪ ተቋማት አመራሮች እንዲሁም ሰራተኞች ከኢትዮጵያ የአካል ድጋፍ አገልግሎት ከገፈርሳ ጉጄ ክፍለ ከተማ ጋር በመተባበር በዛሬ እለት በገፈርሳ ሰው ሰራሽ ሀይቅ ዳርቻ ከ30 ሺህ በላይ ችግኞች በዛሬው እለት ተተክለዋል።
በሸገር ከተማ በገፈርሳ ጉጄ አካባቢ በተካሄደው በዚህ የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር ላይ የጤና ሚኒስትሯ ክብርት ዶክተር መቅደስ ዳባ፣ ሚኒስትር ዴኤታዎች እና የየደረጃው የአካባቢው አመራሮች እንዲሁም የሀገር መከላከያ ሰራዊት አባላትና የማህበረሰብ ክፍሎች ከማለዳው 1 ሰዓት ጀምሮ በመገኘት ችግኝ ተክለዋል።
የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ደረጄ ዱጉማ በዚሁ ወቅት ባደረጉት ንግግር፣ አረንጓዴ አሻራ እና የጤና ዘርፍ የማይለያዩ የአንድ ሳንቲም ሁለት ገጽታዎች መሆናቸውን ገልጸዋል። ችግኝ ለአካባቢ ጥበቃ ብቻ ሳይሆን ለህብረተሰብ ጤና፣ ለንጹህ አየር እና ለምግብ ዋስትና ማሻሻያ ወሳኝ ሚና እንደሚጫወት የጠቆሙት ሚኒስትር ዴኤታው፣ በተለይም ለአዲስ አበባ እና ለአካባቢው ህዝብ የንጹህ ውሃ ምንጭ የሆነውን የገፈርሳ አካባቢን መንከባከብ የሁላችንም ህብረ-ብሄራዊ ሀገራዊ ኃላፊነት እንደሆነ አስገንዝበዋል።
በዕለቱ በቦታው ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የጤና ሚኒስትሯ ክብርት ዶክተር መቅደስ ዳባ በበኩላቸው፣ ኢትዮጵያ የተፈጥሮ አካባቢዋን ለመጠበቅ የምታደርገው ጥረት በንግግር ሳይሆን በተግባር የሚገለጽ መሆኑን አብራርተዋል።
በዕለቱ ሚኒስቴሩ ከተጠሪ ተቋማት ጋር በመሆን ከ30 ሺህ በላይ ችግኞችን የተከለ ሲሆን፣ በክረምቱ የክረምት በጎ ፈቃድ መርሃ-ግብር ደግሞ በሀገር አቀፍ ደረጃ እስከ 250 ሺህ ችግኞችን ለመትከል እና ከ20 ሚሊዮን በላይ ዜጎችን ነጻ የህክምና አገልግሎት ለመስጠት ታቅዶ እየተሰራ እንደሚገኝ ሚኒስትሯ ገልጸዋል።
በመጨረሻም ክብርት ሚኒስትሯ፣ የጤና ባለሙያዎች እና መላው የሀገራችን ህዝብ ቀኑ ሳያልቅ እና ጀምበር ሳትጠልቅ የድርሻቸውን ችግኝ በመትከል የዚህ ታሪካዊ ኩነት አካል እንዲሆኑ ጥሪ አቅርበዋል።
ከችግኝ ተከላው መርሐግብር ባሻገር የኢትዮጵያ የአካል ድጋፍ አገልግሎት በሸገር ከተማ ከ200 በላይ ለሚሆኑ ተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ ተደርጓል።
በጌትነት ተመስገን
📷 ከበደ መክብብ
#ministryofhealth #treeplanting
#climateaction #publichealth
#environmentalhealth #gefersa #cleanenvironment #greenethiopia
#communitysupport
2 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የአፍሪካ ህብረት መረጃ እንደሚያመለክተው ቢያንስ 600,000 ሰዎችን ከገደለው ጦርነት ከአራት ዓመት ባነሰ ጊዜ ውስጥ፣ የፌደራል መንግስት ሰራዊት እና የትግራይ ኃይሎች በሰሜን ትግራይ ድንበር አካባቢ ለወራት ኃይል ሲያከማቹ መቆየታቸው ዳግም ጦርነት ሊቀሰቀስ ይችላል የሚለውን ስጋት አባብሶታል። በዚህም መሰረት በድንበር አካባቢ የተቀሰቀሰውን ውጊያ በመሸሽ በመቶዎች የሚቆጠሩ ከሰሜን ትግራይ ክልል የተፈናቀሉ ኢትዮጵያውያን ባለፉት ሁለት ቀናት ውስጥ ወደ ጎረቤት ሱዳን መግባታቸውን የሱዳን የጸጥታ እና የህክምና ምንጮች ለኤኤፍፒ ተናግረዋል። ይህ የስደተኞች ፍሰት የተከሰተው ሱዳን ራሷ ከሚያዝያ 2023 ጀምሮ በሱዳን ጦር እና በፈጣን ድጋፍ ሰጪ ኃይሎች (RSF) መካከል በሚካሄድ አውዳሚ ጦርነት ውስጥ ባለችበት ወቅት ነው።
አንድ የህዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) አባል እንደገለጹት፣ በኢትዮጵያ ጦር እና በትግራይ ኃይሎች መካከል ከባድ የጦር መሳሪያዎች እና ድሮኖች የታከሉበት ውጊያ በምዕራብ ትግራይ፣ ከሱዳን ድንበር አቅራቢያ በምትገኘው ሸረሪና በተባለችው አካባቢ ቅዳሜ ማለዳ ላይ የተቀሰቀሰ ሲሆን፣ እስከ እሁድ ንጋት 11፡00 ሰዓት (5:00 am) ድረስ ቀጥሎ ነበር። ቅዳሜ ዕለት ህወሓት የኢትዮጵያ ፌደራል መንግስትን ሰፋፊ የእግረኛ ጦር ጥቃቶችን ፈጽሞብኛል ሲል የከሰሰ ሲሆን፣ ባለስልጣናት ለዚህ ክስ ወዲያውኑ የሰጡት ምላሽ የለም። ኤኤፍፒ የህወሓትን ክሶች በገለልተኛ ወገን ማረጋገጥም ሆነ በሸረሪና ውጊያ ውስጥ የተሳተፉትን ኃይሎች በግልጽ መለየት አለመቻሉን ዘግቧል።
በድንበር ከተማዋ ሀምዳይት የሚገኝ አንድ የሱዳን የጸጥታ ምንጭ፣ ከትግራይ ወደ ሱዳን ከገቡት ሰዎች መካከል የቆሰሉ ተዋጊዎች እንደሚገኙበት ገልጿል። በድንበር ጤና ጣቢያ የሚገኝ የህክምና ምንጭ እንዳስታወቀው፣ የቆሰሉት ሰዎች የመጀመሪያ ደረጃ የህክምና እርዳታ ከተደረገላቸው በኋላ በ2020-2022 በነበረው የትግራይ ጦርነት የተፈናቀሉ በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ወደሚገኙበት እና 15 ኪሎ ሜትር ሱዳን ውስጥ ወደሚገኘው አል-ሀሻባ ተዛውረዋል። በሱዳን በኩል የሚገኙ የድንበር አካባቢ ነዋሪዎች በውጊያው ወቅት ከባድ ፍንዳታዎች እና ተከታታይ የተኩስ ልውውጦች ሲሰሙ እንደነበር ዘግበዋል።
ከድንበሩ 40 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በምትገኘው ዋድ አል-ሁለይዋ የተባለች መንደር ነዋሪ የሆነ የዓይን እማኝ፣ ቅዳሜ ማለዳ ላይ ሶስት ኃይለኛ ፍንዳታዎችን መስማቱን ተናግሯል። እማኙ አክሎም፣ ከቀኑ 10፡30 ገደማ ላይ ከባድ የተኩስ ድምጽ ይሰማ እንደነበር እና በአቅራቢያው የምትገኘው የአል-ቁዳይማ መንደር ነዋሪዎች የሰቲት ወንዝን አቋርጠው መሸሻቸውን አስረድቷል። በሀምዳይት የሚገኝ ሌላ የዓይን እማኝ በበኩሉ፣ ቅዳሜን ሙሉ ፍንዳታዎች ይሰሙ እንደነበር እና ከሀምዳይት በስተደቡብ ምዕራብ አቅጣጫ አውሮፕላኖች ሲበሩ መመልከቱን ገልጿል።
ይህ የሰሞኑ ግጭት የተከሰተው በኢትዮጵያ እና ሱዳን መካከል ያለው ግንኙነት ሻክሮ በሚገኝበት ወቅት መሆኑ ሁኔታውን ይበልጥ አሳሳቢ ያደርገዋል። ባለፈው ግንቦት ወር ኢትዮጵያ የሱዳን ጦር ከህወሓት ጋር ግንኙነት ያላቸውን ቅጥረኞች ይደግፋል ስትል የከሰሰች ሲሆን፣ ሱዳን በበኩሏ ኢትዮጵያ ከተባበሩት አረብ ኤምሬቶች ጋር በመቀናጀት ከግዛቷ የድሮን ጥቃቶች እንዲፈጸሙ ፈቅዳለች የሚል ክስ አቅርባለች። የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች የቀረበባትን ክስ ብታስተባብልም፣ የፈጣን ድጋፍ ሰጪ ኃይሎች (RSF) ዋነኛ ደጋፊ ናት ተብላ ትከሰሳለች።
አንድ የህዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) አባል እንደገለጹት፣ በኢትዮጵያ ጦር እና በትግራይ ኃይሎች መካከል ከባድ የጦር መሳሪያዎች እና ድሮኖች የታከሉበት ውጊያ በምዕራብ ትግራይ፣ ከሱዳን ድንበር አቅራቢያ በምትገኘው ሸረሪና በተባለችው አካባቢ ቅዳሜ ማለዳ ላይ የተቀሰቀሰ ሲሆን፣ እስከ እሁድ ንጋት 11፡00 ሰዓት (5:00 am) ድረስ ቀጥሎ ነበር። ቅዳሜ ዕለት ህወሓት የኢትዮጵያ ፌደራል መንግስትን ሰፋፊ የእግረኛ ጦር ጥቃቶችን ፈጽሞብኛል ሲል የከሰሰ ሲሆን፣ ባለስልጣናት ለዚህ ክስ ወዲያውኑ የሰጡት ምላሽ የለም። ኤኤፍፒ የህወሓትን ክሶች በገለልተኛ ወገን ማረጋገጥም ሆነ በሸረሪና ውጊያ ውስጥ የተሳተፉትን ኃይሎች በግልጽ መለየት አለመቻሉን ዘግቧል።
በድንበር ከተማዋ ሀምዳይት የሚገኝ አንድ የሱዳን የጸጥታ ምንጭ፣ ከትግራይ ወደ ሱዳን ከገቡት ሰዎች መካከል የቆሰሉ ተዋጊዎች እንደሚገኙበት ገልጿል። በድንበር ጤና ጣቢያ የሚገኝ የህክምና ምንጭ እንዳስታወቀው፣ የቆሰሉት ሰዎች የመጀመሪያ ደረጃ የህክምና እርዳታ ከተደረገላቸው በኋላ በ2020-2022 በነበረው የትግራይ ጦርነት የተፈናቀሉ በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ወደሚገኙበት እና 15 ኪሎ ሜትር ሱዳን ውስጥ ወደሚገኘው አል-ሀሻባ ተዛውረዋል። በሱዳን በኩል የሚገኙ የድንበር አካባቢ ነዋሪዎች በውጊያው ወቅት ከባድ ፍንዳታዎች እና ተከታታይ የተኩስ ልውውጦች ሲሰሙ እንደነበር ዘግበዋል።
ከድንበሩ 40 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በምትገኘው ዋድ አል-ሁለይዋ የተባለች መንደር ነዋሪ የሆነ የዓይን እማኝ፣ ቅዳሜ ማለዳ ላይ ሶስት ኃይለኛ ፍንዳታዎችን መስማቱን ተናግሯል። እማኙ አክሎም፣ ከቀኑ 10፡30 ገደማ ላይ ከባድ የተኩስ ድምጽ ይሰማ እንደነበር እና በአቅራቢያው የምትገኘው የአል-ቁዳይማ መንደር ነዋሪዎች የሰቲት ወንዝን አቋርጠው መሸሻቸውን አስረድቷል። በሀምዳይት የሚገኝ ሌላ የዓይን እማኝ በበኩሉ፣ ቅዳሜን ሙሉ ፍንዳታዎች ይሰሙ እንደነበር እና ከሀምዳይት በስተደቡብ ምዕራብ አቅጣጫ አውሮፕላኖች ሲበሩ መመልከቱን ገልጿል።
ይህ የሰሞኑ ግጭት የተከሰተው በኢትዮጵያ እና ሱዳን መካከል ያለው ግንኙነት ሻክሮ በሚገኝበት ወቅት መሆኑ ሁኔታውን ይበልጥ አሳሳቢ ያደርገዋል። ባለፈው ግንቦት ወር ኢትዮጵያ የሱዳን ጦር ከህወሓት ጋር ግንኙነት ያላቸውን ቅጥረኞች ይደግፋል ስትል የከሰሰች ሲሆን፣ ሱዳን በበኩሏ ኢትዮጵያ ከተባበሩት አረብ ኤምሬቶች ጋር በመቀናጀት ከግዛቷ የድሮን ጥቃቶች እንዲፈጸሙ ፈቅዳለች የሚል ክስ አቅርባለች። የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች የቀረበባትን ክስ ብታስተባብልም፣ የፈጣን ድጋፍ ሰጪ ኃይሎች (RSF) ዋነኛ ደጋፊ ናት ተብላ ትከሰሳለች።
2 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) በአሜሪካ ኦሪገን ግዛት፣ ዩጂን ከተማ በሚካሄደው 21ኛው የዓለም ከ20 ዓመት በታች አትሌቲክስ ሻምፒዮና ላይ ሀገራቸውን በኩራት እንዲወክሉ የተመረጡ 23 ወጣት ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ባጋጠማቸው የቪዛ መዘግየት ምክንያት ከፍተኛ የሆነ ስጋት ውስጥ ወድቀዋል። ውድድሩ ሊጀመር የሳምንት ዕድሜ ብቻ በቀረው በዚህ ወሳኝ ሰዓት፣ የልዑካን ቡድኑ ወደ አሜሪካ ለመጓዝ ያቀረበው የቪዛ ጥያቄ እስካሁን ድረስ ምንም ዓይነት ምላሽ አለማግኘቱን የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን በይፋ አስታውቋል።
ምንም እንኳን የፌዴሬሽኑ የውስጥ ምንጮች የቪዛ ጥያቄው በቅርቡ ምላሽ ያገኛል የሚል ተስፋ እንዳላቸው ቢገልጹም፣ መሬት ላይ ያለው የጊዜ እጥረት ግን ጉዳዩን እጅግ አሳሳቢ ያደርገዋል። ኢትዮጵያን ጨምሮ ከ190 ሀገራት የተውጣጡ 1,700 አትሌቶች በሚሳተፉበት በዚህ ግዙፍ መድረክ ላይ፣ የኢትዮጵያ ተወዳዳሪዎች በመጨረሻው ሰዓት በቪዛ መጓተት ምክንያት ወደ ኋላ መጎተታቸው በአትሌቶቹ የስነ-ልቦና እና የአካል ዝግጅት ላይ ትልቅ ጫና ፈጥሯል።
ይህ ዓይነቱ አስተዳደራዊ እና ዲፕሎማሲያዊ መጓተት የሀገሪቱን ስፖርታዊ ውክልና ወደ አደገኛ ደረጃ ያሸጋገረ ክስተት ነው። ወጣት አትሌቶች ለዓመታት ያፈሰሱት ላብ እና ያደረጉት ከፍተኛ ልምምድ በሩጫ ሜዳ ላይ ሳይሆን በኤምባሲ ደጃፍ ላይ በከንቱ እንዳይቀር ፈጣን ርብርብ ማድረግ ወሳኝ መሆኑን የጉዳዩ አሳሳቢነት በግልጽ ያሳያል። የልዑካን ቡድኑ እና አትሌቶቹ ከውድድሩ ውጥረት በዘለለ የጉዞ እርግጠኛ አለመሆን ፈተና ውስጥ መውደቃቸው የስፖርቱን ማህበረሰብ ክፉኛ እያሳሰበ ይገኛል።
ምንም እንኳን የፌዴሬሽኑ የውስጥ ምንጮች የቪዛ ጥያቄው በቅርቡ ምላሽ ያገኛል የሚል ተስፋ እንዳላቸው ቢገልጹም፣ መሬት ላይ ያለው የጊዜ እጥረት ግን ጉዳዩን እጅግ አሳሳቢ ያደርገዋል። ኢትዮጵያን ጨምሮ ከ190 ሀገራት የተውጣጡ 1,700 አትሌቶች በሚሳተፉበት በዚህ ግዙፍ መድረክ ላይ፣ የኢትዮጵያ ተወዳዳሪዎች በመጨረሻው ሰዓት በቪዛ መጓተት ምክንያት ወደ ኋላ መጎተታቸው በአትሌቶቹ የስነ-ልቦና እና የአካል ዝግጅት ላይ ትልቅ ጫና ፈጥሯል።
ይህ ዓይነቱ አስተዳደራዊ እና ዲፕሎማሲያዊ መጓተት የሀገሪቱን ስፖርታዊ ውክልና ወደ አደገኛ ደረጃ ያሸጋገረ ክስተት ነው። ወጣት አትሌቶች ለዓመታት ያፈሰሱት ላብ እና ያደረጉት ከፍተኛ ልምምድ በሩጫ ሜዳ ላይ ሳይሆን በኤምባሲ ደጃፍ ላይ በከንቱ እንዳይቀር ፈጣን ርብርብ ማድረግ ወሳኝ መሆኑን የጉዳዩ አሳሳቢነት በግልጽ ያሳያል። የልዑካን ቡድኑ እና አትሌቶቹ ከውድድሩ ውጥረት በዘለለ የጉዞ እርግጠኛ አለመሆን ፈተና ውስጥ መውደቃቸው የስፖርቱን ማህበረሰብ ክፉኛ እያሳሰበ ይገኛል።
2 days ago
ለትውልድ የሚሻገር አኩሪ ታሪክ የሚጻፍበት የአንድ ጀንበር ችግኝ ተከላ
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 26፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ኢትዮጵያ ከ2011 ዓ.ም ጀምሮ በአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር አማካኝነት የደን ሀብቷን ለማሳደግ፣ የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖዎችን የመቋቋም ጉዞ ዛሬ ላይ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚጠቀስ አርአያነት ያለው ተግባር ሆኗል።
ይህ በየዓመቱ በከፍተኛ ህዝባዊ ንቅናቄ የሚታወቀው መርሐ ግብር የተፈጥሮ ሚዛንን በመጠበቅ የወደፊት ትውልድ ተስፋን በጽኑ መሠረት ላይ የሚያንጽ ብሔራዊ ንቅናቄ ነው።
በየዓመቱ የሚካሄደው የአንድ ጀንበር የችግኝ ተከላ መርሐ ግብር ሚሊየኖች ከዳር እስከ ዳር በዝናብና በብርድ ሳይበገሩ በመዝመት ምድርን የሚያለመልሙበት መድረክ ሆኗል።
ነገ ማለዳ በይፋ ለሚጀመረው የዘንድሮው የአንድ ጀንበር የችግኝ ተከላ መርሐ ግብር እንደ ሀገር አስፈላጊው ዝግጅት ተደርጓል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ባስተላለፉት መልዕክት፥ የነገው መርሐ ግብር የኢትዮጵያውያን ክንድ ተባብሮ፣ በአንድ ጀንበር 800 ሚሊየን ችግኞችን በመትከል ሌላ ታሪክ የምንሰራበት ነው ብለዋል፡፡
የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር የደን ሽፋንን በእጥፍ ከማሳደግ ባሻገር፣ የአፈር መሸርሸርን ለመከላከል፣ የውሃ አካላትን ለማበልጸግና የግብርና ምርታማነትን በዘላቂነት ለማሳደግ የጎላ ሚና ይጫወታል።
ከዚሁ ጎን ለጎን የሚተከሉት ችግኞች የምግብ ዋስትናን የሚያረጋግጡ የፍራፍሬ ተክሎች እንዲሁም የኢኮኖሚ ጥቅም የሚሰጡ የዛፍ ዝርያዎችን ያካተቱ በመሆናቸው ለሀገራችን የኢኮኖሚ እድገት አዎንታዊ አስተዋጽኦ ያበረክታሉ።
ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የችግኝ ተከላ ዘመቻዎች ሕዝቡ ባደረገው ከፍተኛ ተሳትፎ መርሐ ግብሩ ከአካባቢ ጥበቃ ባለፈ የሀገራዊ አንድነት መገለጫ መሆን ችሏል።
800 ሚሊየን ችግኞችን በአንድ ጀንበር የመትከል ዘመቻው ለኢትዮጵያ የአረንጓዴ ልማት፣ የአየር ንብረት ተጽዕኖን ለመቋቋም፣ ለምግብ ዋስትናና ለትውልድ ተሻጋሪ የተፈጥሮ ሀብት ግንባታ የሚያበረክተውን ድርሻ የበለጠ የሚያጎላ ነው።
እያንዳንዱ ዜጋ ከጫፍ እስከ ጫፍ በመነሳት የድርሻውን እንዲወጣ የሚጠይቀው ይህ ሀገራዊ ጥሪ በከተማም ሆነ በገጠር የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን በማለዳው በመውጣት የራሳቸውን ታሪካዊ ዐሻራ እንዲያኖሩ በር የከፈተ ሆኗል።
ይህ እቅድ የቁጥር ጉዳይ ብቻ ሳይሆን የጽናት፣ የህብረትና የልማት ታላቅ መገለጫ በመሆኑ ኢትዮጵያውያን በተፈጥሮ ሀብታቸው ላይ አዲስ ሕይወት የሚዘሩበት፣ ለቀጣዩ ትውልድ ለም እና አረንጓዴ ሀገር የሚያስረክቡበት ታሪካዊ አጋጣሚ ነው።
ችግኞችን ከመትከል ባለፈ የመንከባከብና የመጠበቅ ባሕልን ማሳደግ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር ዋነኛ ምሰሶ በመሆኑ እያንዳንዱ የተተከለ ችግኝ ጸድቆ ለፍሬ እንዲበቃ ሁሉም አካላት የተቀናጀ ጥረትና ክትትል ማድረግ ይጠበቅባቸዋል።
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 26፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ኢትዮጵያ ከ2011 ዓ.ም ጀምሮ በአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር አማካኝነት የደን ሀብቷን ለማሳደግ፣ የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖዎችን የመቋቋም ጉዞ ዛሬ ላይ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚጠቀስ አርአያነት ያለው ተግባር ሆኗል።
ይህ በየዓመቱ በከፍተኛ ህዝባዊ ንቅናቄ የሚታወቀው መርሐ ግብር የተፈጥሮ ሚዛንን በመጠበቅ የወደፊት ትውልድ ተስፋን በጽኑ መሠረት ላይ የሚያንጽ ብሔራዊ ንቅናቄ ነው።
በየዓመቱ የሚካሄደው የአንድ ጀንበር የችግኝ ተከላ መርሐ ግብር ሚሊየኖች ከዳር እስከ ዳር በዝናብና በብርድ ሳይበገሩ በመዝመት ምድርን የሚያለመልሙበት መድረክ ሆኗል።
ነገ ማለዳ በይፋ ለሚጀመረው የዘንድሮው የአንድ ጀንበር የችግኝ ተከላ መርሐ ግብር እንደ ሀገር አስፈላጊው ዝግጅት ተደርጓል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ባስተላለፉት መልዕክት፥ የነገው መርሐ ግብር የኢትዮጵያውያን ክንድ ተባብሮ፣ በአንድ ጀንበር 800 ሚሊየን ችግኞችን በመትከል ሌላ ታሪክ የምንሰራበት ነው ብለዋል፡፡
የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር የደን ሽፋንን በእጥፍ ከማሳደግ ባሻገር፣ የአፈር መሸርሸርን ለመከላከል፣ የውሃ አካላትን ለማበልጸግና የግብርና ምርታማነትን በዘላቂነት ለማሳደግ የጎላ ሚና ይጫወታል።
ከዚሁ ጎን ለጎን የሚተከሉት ችግኞች የምግብ ዋስትናን የሚያረጋግጡ የፍራፍሬ ተክሎች እንዲሁም የኢኮኖሚ ጥቅም የሚሰጡ የዛፍ ዝርያዎችን ያካተቱ በመሆናቸው ለሀገራችን የኢኮኖሚ እድገት አዎንታዊ አስተዋጽኦ ያበረክታሉ።
ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የችግኝ ተከላ ዘመቻዎች ሕዝቡ ባደረገው ከፍተኛ ተሳትፎ መርሐ ግብሩ ከአካባቢ ጥበቃ ባለፈ የሀገራዊ አንድነት መገለጫ መሆን ችሏል።
800 ሚሊየን ችግኞችን በአንድ ጀንበር የመትከል ዘመቻው ለኢትዮጵያ የአረንጓዴ ልማት፣ የአየር ንብረት ተጽዕኖን ለመቋቋም፣ ለምግብ ዋስትናና ለትውልድ ተሻጋሪ የተፈጥሮ ሀብት ግንባታ የሚያበረክተውን ድርሻ የበለጠ የሚያጎላ ነው።
እያንዳንዱ ዜጋ ከጫፍ እስከ ጫፍ በመነሳት የድርሻውን እንዲወጣ የሚጠይቀው ይህ ሀገራዊ ጥሪ በከተማም ሆነ በገጠር የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን በማለዳው በመውጣት የራሳቸውን ታሪካዊ ዐሻራ እንዲያኖሩ በር የከፈተ ሆኗል።
ይህ እቅድ የቁጥር ጉዳይ ብቻ ሳይሆን የጽናት፣ የህብረትና የልማት ታላቅ መገለጫ በመሆኑ ኢትዮጵያውያን በተፈጥሮ ሀብታቸው ላይ አዲስ ሕይወት የሚዘሩበት፣ ለቀጣዩ ትውልድ ለም እና አረንጓዴ ሀገር የሚያስረክቡበት ታሪካዊ አጋጣሚ ነው።
ችግኞችን ከመትከል ባለፈ የመንከባከብና የመጠበቅ ባሕልን ማሳደግ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር ዋነኛ ምሰሶ በመሆኑ እያንዳንዱ የተተከለ ችግኝ ጸድቆ ለፍሬ እንዲበቃ ሁሉም አካላት የተቀናጀ ጥረትና ክትትል ማድረግ ይጠበቅባቸዋል።
Sponsored by
Surafel
2 days ago
ከባንኮክ እስከ ፉኬትና ፓታያ ( በወፍ በረር ... )
* ታይላንድ በዓይኔ ያየኋት፣ በእጄ የነካኋት፣ በልቤ የቀረች የባሕር ነፍስ…!
በገብረማርያም ይርጋ [ የጉዞ ማስታወሻ ]
#ethiopia | እውነተኛ ጉዞ የሚጀምረው ሰው ከራሱ ጋር ሲገናኝ ነው። እውነተኛ ጉዞ አውሮፕላኑ ሲያርፍ አያበቃም፤ ትዝታ በልብ ውስጥ ሲቀጥል እንጂ።
ዓለም አቀፍ የባህልና ጥበባት ልማት ሙያዊ ሽልማቴን ለመቀበል ወደ ደቡብ ምስራቅ እስያዋ እንቁ — ታይላንድ — ስጓዝ፣ አእምሮዬን የሞላው የጉዞው ዓላማ ብቻ ነበር።
ነገር ግን እግሬ የታይላንድን ምድር ሲረግጥ የተቀበለኝ የከተማዋ የሲሚንቶና የአስፋልት ግለት ወይም የዘመናዊነት ጫጫታ አልነበረም፤ ከሩቅ የባሕር ጥልቀት እየነፈሰ በፊቴ ላይ እንደ አሮጌ ወዳጅ ቀስ ብሎ የተራመደው ቀዝቃዛ የባሕር ነፋስ እንጂ።
ደቡባዊቷ እንቁ — ፉኬትና የፓታያ ሞገዶች
በውሃው ላይ የተበተኑት ባህላዊ የረጅም ጅራት (Long-tail) ጀልባዎች፣ የፀሐይ ወርቃማ ብርሃን በውሃው ላይ ሲያርፍ የሚፈጥረው ብልጭታ፣ የሰማዩና የባሕሩ አድማስ ላይ መገናኘት… እነዚህ ሁሉ ተደምረው እንደ ተአምራዊ ሕልም ይታዩ ነበር። በዚያ ቅጽበት እኔ ባሕሩን አልተመለከትኩትም፤ ባሕሩ እኔን በጥልቀቱ እየተመለከተኝ ነበር።
በጄትስኪ (Jet Ski) አየርና ውሃውን ሰንጥቄ ስነጥቅ፣ የነጭ አረፋ መስመር ከኋላዬ እንደ ግጥም ይሰመር ነበር። በወቅቱ የተረዳሁት ነገር ቢኖር—ፍጥነት ሰውን ከምድር አያርቀውም፤ ይልቁንም በውስጡ የተሸሸገውን እውነተኛ ደስታ ቅርብ ያደርገዋል!
የሰማይ ላይ በረራ (Parasailing)፦ገመዱ ተለቆ ሰማይ ሲከፈትልኝ፣ ከላይ ሆኜ ስመለከት ባሕሩ እንደ ታላቅ ሰማያዊ መስታወት ተንጣሎ ታየኝ።
በዚያ ከፍታ ላይ ዓለም ትንሽ ስትሆን፣ ሰውን የሚያስጨንቀው የዕለት ተዕለት ጭነቷም አብሮ ትንሽ ይሆናል። እንደ ልጅ ሆኜ የነፋሱን ሹክሹክታ ብቻ እሰማ ነበር… ወጣሁ፣ ተነጠቅሁ!
በፉኬት ነጭ አሸዋው በእግር ስር ሲለሰልስ፣ ግልጽና ሰማያዊው ውሃ እስከ ጉልበት ሲደርስ፣ ፀሐይ በቆዳ ላይ ወርቃማ ሙቀቷን ስትረጭ ዓለምና ጭንቋ ሙሉ በሙሉ የተረሱ ይመስላሉ።
የባንኮክ ድቅቅ ያለ ውበትና የሌሊት ከዋክብት
ባንኮክ በቀን በገዥና ሻጭ፣ በበዛ እንቅስቃሴና ህይወት ስትደምቅ፤ ሌሊት ደግሞ በምድር ላይ እንደወረዱ ከዋክብት የሚያበሩ መብራቶች ያሏት አስማተኛ ከተማ ትሆናለች። የከተማዋ ሰማይ ጠቀስ ህንፃዎች መብራት በውሃው ላይ ሲሰበር፣ ወርቅና አልማዝ በውሃ ላይ የተበተነ ይመስላል።
በቻኦ ፕራያ (Chao Phraya) ወንዝ ላይ ያለ ምሽት
ከጉዞዬ ሁሉ በላይ በልቤ የተቀረፀው በመርከብ ላይ ያሳለፍኩት ምሽት ነው።
የምስራቃዊው የሙዚቃ ዜማ፣ የሰዎች ወዳጃዊ ሳቅ፣ ጣፋጭ እራት…
በወንዙ ላይ እያለፈች ባለው መርከብ ላይ ሆነን በከተማዋ መብራቶች መካከል ስንሳፈፍ፣ በአንድ ቅጽበት ውስጥ ዓለም በሙሉ የተሰበሰበች ያህል ተሰማኝ።
በዚያ ምሽት አንድ ታላቅ እውነት ተረዳሁ—ደስታ ታላቅና ውስብስብ ነገር አይፈልግም፤ በሙሉ ልብ የሚኖር አንድ ቅጽበት ብቻ ይበቃዋል።
በሻንጣ ያልተያዘ፣ በልብ የተያዘ ሀብት
ታይላንድ ከዚህ በኋላ ከእኔ አትጠፋም፤ በውስጤ ዘላለማዊ ቦታዋን ይዛለች። የፓታያ ነፋስ አሁንም በፊቴ ላይ ይነፍሳል፣ የፉኬት ሞገድ በልቤ ይመታል፣ የባንኮክ የሌሊት መብራት በዓይኔ ላይ ይበራል።
ከዚህ ጉዞ ስመለስ በሻንጣዬ ውስጥ ያሸግኩት ያበደሩኝን ልብስ ብቻ አይደለም፤
የሞገዱን ዘላለማዊ ድምፅ፣ ...
የፀሐይዋን አፍቃሪ ሙቀት፣ ...
የአሸዋውን ልስላሴ፣ ...
የሌሊት መብራቶቿን ብሩህነት፣ ...
እና ...
የልቤን ሙሉ ደስታ ነው።
እውነተኛ ጉዞ አውሮፕላኑ ሲያርፍ አይጨርስም፤ ትዝታው በልባችን ውስጥ መኖር ሲቀጥል እንጂ!
ታይላንድ በዓይኔ ያየኋት፣ በእጄ የነካኋት፣ በልቤ የቀረች የባሕር ነፍስ…!
2 days ago
መልካም ጉዞ...
ተፃፈ በመሐሪ ነጋሽ
(የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ኮሚኒኬሽን )
#ethiopia | ዛሬ ማምሻውን የኢትዮጵያ ከ20 ዓመት በታች አትሌቲክስ ልዑክ ቡድናችንን በከፍተኛ ኩራትና በመልካም ምኞት ወደ አሜሪካ ኦሪገን ሸኝተናል።
የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን አትሌቶቻችን በተሟላ ዝግጅት ወደ ሻምፒዮናው እንዲያቀኑ ሱሉልታ በሚገኘው የጀግናው ኦሊምፒያን አትሌት ቀነኒሳ በቀለ ሆቴል በማሳረፍ አስፈላጊውን ድጋፍ፣ ክትትልና ዝግጅት ሲያደርግ ቆይቷል።
የቀነኒሳ በቀለ ሆቴልም አትሌቶቻችንን እንደቤተሰቦቹ በመቀበል፣ በፍቅር፣ በአክብሮትና በልዩ እንክብካቤ እስከ ሽኝታቸው ድረስ አግዟቸዋል።
ለዚህ ውድ አስተዋፅኦ ከልብ የመነጨ ምስጋና ተቀበሉ
ዓለም የሚጠብቀው ሻምፒዮና 21ኛው የዓለም ከ20 ዓመት በታች (World Athletics U20 Championships) ሻምፒዮና ....
በአሜሪካ ኦሪገን ግዛት ዩጂን ከተማ በሚገኘው ታሪካዊው ሄይዋርድ ፊልድ ከሐምሌ 29 እስከ ነሐሴ 3 ይካሄዳል።
ከ1,700 በላይ ወጣት አትሌቶች ከ190 የሚጠጉ አገራት በ44 የውድድር ዓይነቶች ላይ ይፎካከራሉ።
ዩጂን ከተማ በግምት 180,000 የሚጠጋ ህዝብ ያላት ብትሆንም፣ በዓለም ላይ "Track Town USA" በሚል ስም የምትታወቅ የአትሌቲክስ ዋና መዲና ናት።
የሻምፒዮናው ትኬቶች በፍጥነት እየተሸጡ እንደሆነ አዘጋጆቹ ገልጸዋል፣ ውድድሩም በብዙ የዓለም አቀፍ የቴሌቪዥን ኔትወርኮች፣ ዲጂታል መድረኮች እና በመቶዎች የሚቆጠሩ የስፖርት ጋዜጠኞች ይሸፈናል። የዚህ ውድድር ቀደምት እትሞች በ140 በላይ አገራት በቴሌቪዥን ተሰራጭተው 16 ሚሊዮን በላይ የተጠራቀመ የቲቪ ተመልካች ደርሰው ነበር።
በ2024 በፔሩ ሊማ በተካሄደው 20ኛው ሻምፒዮና ኢትዮጵያ 6 የወርቅ፣ 1 የብር እና 2 የነሐስ ሜዳሊያዎችን በማሸነፍ በአጠቃላይ 9 ሜዳሊያዎችን በመሰብሰብ በዓለም 2ኛ ደረጃን ማስመዝገቧ ይታወሳል።
ዘንድሮም አትሌቶቻችን በ5000 ሜትር፣ 3000 ሜትር፣ 1500 ሜትር፣ 800 ሜትር፣ 3000 ሜትር መሰናክል፣ 400 ሜትር እና በርምጃ ውድድሮች ላይ የኢትዮጵያን ስም በክብር ለማስጠራት ዝግጁ ናቸው።
ለጀግኖቻችን...
ውድ አትሌቶቻችን!
ከእናንተ ጋር የሚጓዘው የኢትዮጵያ 60 ዓመታትን ያስቆጠረ የድል ታሪክ ነው፤ የአበበ ቢቂላ ጨምሮ
የብዙ ጀግኖች የድል አሻራ ነው።
ኢትዮጵያውያን ልብ ከእናንተ ጋር ነው። በእግራችሁ የምትሮጡት ለራሳችሁ ብቻ ሳይሆን ለሀገራችሁ፣ ለሕዝባችሁ እና ለመጪው ትውልድ ነው።
መልካም ጉዞ!
መልካም ውድድር!
መልካም ዕድል! 🇪🇹❤️
ተፃፈ በመሐሪ ነጋሽ
(የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ኮሚኒኬሽን )
#ethiopia | ዛሬ ማምሻውን የኢትዮጵያ ከ20 ዓመት በታች አትሌቲክስ ልዑክ ቡድናችንን በከፍተኛ ኩራትና በመልካም ምኞት ወደ አሜሪካ ኦሪገን ሸኝተናል።
የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን አትሌቶቻችን በተሟላ ዝግጅት ወደ ሻምፒዮናው እንዲያቀኑ ሱሉልታ በሚገኘው የጀግናው ኦሊምፒያን አትሌት ቀነኒሳ በቀለ ሆቴል በማሳረፍ አስፈላጊውን ድጋፍ፣ ክትትልና ዝግጅት ሲያደርግ ቆይቷል።
የቀነኒሳ በቀለ ሆቴልም አትሌቶቻችንን እንደቤተሰቦቹ በመቀበል፣ በፍቅር፣ በአክብሮትና በልዩ እንክብካቤ እስከ ሽኝታቸው ድረስ አግዟቸዋል።
ለዚህ ውድ አስተዋፅኦ ከልብ የመነጨ ምስጋና ተቀበሉ
ዓለም የሚጠብቀው ሻምፒዮና 21ኛው የዓለም ከ20 ዓመት በታች (World Athletics U20 Championships) ሻምፒዮና ....
በአሜሪካ ኦሪገን ግዛት ዩጂን ከተማ በሚገኘው ታሪካዊው ሄይዋርድ ፊልድ ከሐምሌ 29 እስከ ነሐሴ 3 ይካሄዳል።
ከ1,700 በላይ ወጣት አትሌቶች ከ190 የሚጠጉ አገራት በ44 የውድድር ዓይነቶች ላይ ይፎካከራሉ።
ዩጂን ከተማ በግምት 180,000 የሚጠጋ ህዝብ ያላት ብትሆንም፣ በዓለም ላይ "Track Town USA" በሚል ስም የምትታወቅ የአትሌቲክስ ዋና መዲና ናት።
የሻምፒዮናው ትኬቶች በፍጥነት እየተሸጡ እንደሆነ አዘጋጆቹ ገልጸዋል፣ ውድድሩም በብዙ የዓለም አቀፍ የቴሌቪዥን ኔትወርኮች፣ ዲጂታል መድረኮች እና በመቶዎች የሚቆጠሩ የስፖርት ጋዜጠኞች ይሸፈናል። የዚህ ውድድር ቀደምት እትሞች በ140 በላይ አገራት በቴሌቪዥን ተሰራጭተው 16 ሚሊዮን በላይ የተጠራቀመ የቲቪ ተመልካች ደርሰው ነበር።
በ2024 በፔሩ ሊማ በተካሄደው 20ኛው ሻምፒዮና ኢትዮጵያ 6 የወርቅ፣ 1 የብር እና 2 የነሐስ ሜዳሊያዎችን በማሸነፍ በአጠቃላይ 9 ሜዳሊያዎችን በመሰብሰብ በዓለም 2ኛ ደረጃን ማስመዝገቧ ይታወሳል።
ዘንድሮም አትሌቶቻችን በ5000 ሜትር፣ 3000 ሜትር፣ 1500 ሜትር፣ 800 ሜትር፣ 3000 ሜትር መሰናክል፣ 400 ሜትር እና በርምጃ ውድድሮች ላይ የኢትዮጵያን ስም በክብር ለማስጠራት ዝግጁ ናቸው።
ለጀግኖቻችን...
ውድ አትሌቶቻችን!
ከእናንተ ጋር የሚጓዘው የኢትዮጵያ 60 ዓመታትን ያስቆጠረ የድል ታሪክ ነው፤ የአበበ ቢቂላ ጨምሮ
የብዙ ጀግኖች የድል አሻራ ነው።
ኢትዮጵያውያን ልብ ከእናንተ ጋር ነው። በእግራችሁ የምትሮጡት ለራሳችሁ ብቻ ሳይሆን ለሀገራችሁ፣ ለሕዝባችሁ እና ለመጪው ትውልድ ነው።
መልካም ጉዞ!
መልካም ውድድር!
መልካም ዕድል! 🇪🇹❤️
2 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) መብራት የተቋረጠባቸው ሱዳናዊያን መንገድ ዘግተው ዋሉ፡፡ በሱዳን ቀይ ባህር ግዛት የሚገኙ ነዋሪዎች የመብራት አገልግሎት የተቋረጠባቸው መሆኑን ተከትሎ ከአርብ እለት ጀምሮ ተቃውሞ እያሰሙ ይገኛሉ፡፡ ይህ ተቃውሞ በትላንትናው እለትም ቀጥሎ ፖርት ሱዳንን ከዋና ከተማዋ ካርቱም ጋር የሚያገናኘውን መንገድ ዘግተው መዋላቸውን ሱዳን ትሪቢዩን ዘግቧል፡፡
ተቃዋሚዎቹ በግዛታቸው ውስጥ በአሁኑ ወቅት የተከሰተውን ሀይለኛ ሙቀት ከግምት ውስጥ በማስገባት መንግስት የመብራት አገልግሎቱ በአስቸኳይ የሚመለስበትን እርምጃ እንዲወስድ እየጠየቁ ናቸው፡፡ እንደዘገባው በቀይ ባህር ግዛት ከፍተኛ የሙቀት መጠን እየተመዘገበ ሲሆን አንዳንድ ቤተሰቦች ቤታቸውን ጥለው ቀዝቃዛ ወደሆኑ ግዛቶች በመሄድ ላይ ናቸው፡፡ በርካታ የግዛቱ ነዋሪ ግን በተፈጠረው የኤሌክትሪክ መቋረጥ የተነሳ የከፋ ህይወትን ለማሳለፍ ተገደዋል፡፡
አንድ የአካባቢው ነዋሪ ለሱዳን ትሪቢዩን ሲናገሩ የመብራት መጥፋቱ መሰረታዊ አገልግሎቶች እንዲቋረጡ ማድረጉን ገልፀው በከፍተኛ ሙቀት ውስጥ የነዋሪው የእለት ተእለት ኑሮውን የባሰ እንዳደረገው አስረድተዋል፡፡ ነዋሪው ፖርት ሱዳንን ወደዋና ከተማዋና ሌሎችም ማእከላዊ የአገሪቱ ክፍሎች የሚወስደውን ዋና መንገድ ለመዝጋት የተገደደው በዚህ የተነሳ መሆኑንም ገልፀዋል፡፡
ሌላ ስማቸው እንዲገለፅ ያልፈለጉ ነዋሪ በበኩላቸው መንገድ የመዝጋት እርምጃው የተወሰደው ለበርካታ ጊዜ ችግሩ እንዲስተካከል ለመንግስት ያቀረቡት አቤቱታ ምላሽ በማጣቱ መሆኑን ገልፀዋል፡፡ ከፍተኛ ሙቀት ባለበት ሁኔታ የመብራት መቆራረጥ መፈጠሩ በተለይ ህፃናትና አረጋዊያን ላይ የጤና ችግር እያስከተ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡ የሜትሮሎጂ መረጃዎች በቀይ ባህር ግዛት በሚቀጥሉት ቀናትም የሙቀት መጠኑ እንደሚጨምር ይገልፃሉ፡፡
ተቃዋሚዎቹ በግዛታቸው ውስጥ በአሁኑ ወቅት የተከሰተውን ሀይለኛ ሙቀት ከግምት ውስጥ በማስገባት መንግስት የመብራት አገልግሎቱ በአስቸኳይ የሚመለስበትን እርምጃ እንዲወስድ እየጠየቁ ናቸው፡፡ እንደዘገባው በቀይ ባህር ግዛት ከፍተኛ የሙቀት መጠን እየተመዘገበ ሲሆን አንዳንድ ቤተሰቦች ቤታቸውን ጥለው ቀዝቃዛ ወደሆኑ ግዛቶች በመሄድ ላይ ናቸው፡፡ በርካታ የግዛቱ ነዋሪ ግን በተፈጠረው የኤሌክትሪክ መቋረጥ የተነሳ የከፋ ህይወትን ለማሳለፍ ተገደዋል፡፡
አንድ የአካባቢው ነዋሪ ለሱዳን ትሪቢዩን ሲናገሩ የመብራት መጥፋቱ መሰረታዊ አገልግሎቶች እንዲቋረጡ ማድረጉን ገልፀው በከፍተኛ ሙቀት ውስጥ የነዋሪው የእለት ተእለት ኑሮውን የባሰ እንዳደረገው አስረድተዋል፡፡ ነዋሪው ፖርት ሱዳንን ወደዋና ከተማዋና ሌሎችም ማእከላዊ የአገሪቱ ክፍሎች የሚወስደውን ዋና መንገድ ለመዝጋት የተገደደው በዚህ የተነሳ መሆኑንም ገልፀዋል፡፡
ሌላ ስማቸው እንዲገለፅ ያልፈለጉ ነዋሪ በበኩላቸው መንገድ የመዝጋት እርምጃው የተወሰደው ለበርካታ ጊዜ ችግሩ እንዲስተካከል ለመንግስት ያቀረቡት አቤቱታ ምላሽ በማጣቱ መሆኑን ገልፀዋል፡፡ ከፍተኛ ሙቀት ባለበት ሁኔታ የመብራት መቆራረጥ መፈጠሩ በተለይ ህፃናትና አረጋዊያን ላይ የጤና ችግር እያስከተ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡ የሜትሮሎጂ መረጃዎች በቀይ ባህር ግዛት በሚቀጥሉት ቀናትም የሙቀት መጠኑ እንደሚጨምር ይገልፃሉ፡፡
2 days ago
የአረንጓዴ ዐሻራ የሰባት ዓመታት ሰባት አንኳር ስኬቶች
*************
አረንጓዴ ዐሻራ በኢትዮጵያ ምድር ከተጀመረበት ጊዜ አንስቶ ባለፉት ሰባት ዓመታት፣ ሀገራችንን ከአፈር መሸርሸር እና ከበረሃማነት የመታደግ ሀገራዊ ራዕይ ብቻ ሳይሆን፤ የምድርን ሕይወት የሚያድስ፣ የዜጎችን ሥነ-ልቦናዊ አስተሳሰብ የሚቀርጽ እና ኢኮኖሚያዊ አቅም የሚገነባ ታላቅ ሕዝባዊ ንቅናቄ ሆኖ ዘልቋል።
ይህ ሀገራዊ የሕልውና ጥረት ከሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ ስትራቴጂዎች ጋር ተናብቦ ባለፉት ሰባት ዓመታት ያስመዘገባቸው ሰባት ዋና ዋና ተጨባጭ ስኬቶች እንደሚከተለው ተተንትነዋል።
1. የችግኝ ብዛትን ከጽድቀት ምጣኔ ጋር ያጣመረ አዲስ ታሪካዊ ሽግግር
ባለፉት ሰባት ዓመታት በቢሊዮኖች የሚቆጠሩ ችግኞች መተከላቸው ብቻ ሳይሆን፣ የተከላው ዋና ትኩረት ወደ ጥራት እና ድኅረ-ተከላ እንክብካቤ በማደጉ የችግኞች ጽድቀት ምጣኔ ከ80 በመቶ በላይ ማደግ ችሏል።
ይህም ቀደም ሲል የነበረውን "መተከል እንጂ አለመጽደቅ" የሚል የብክነት ታሪክን በመቀየር በቆላ እና በደጋ አካባቢዎች የተጎዱ መሬቶች በፍጥነት አረንጓዴ እንዲለብሱ እና ሥነ-ምኅዳራዊ ሚዛን እንዲጠበቅ አድርጓል።
2. ከአካባቢ ጥበቃ ወደ የምግብ ዋስትና የተደረገ መዋቅራዊ የኢኮኖሚ ሽግግር
አረንጓዴ ዐሻራ ከተፈጥሮ የደን ዛፎች ባሻገር እንደ አቮካዶ፣ ማንጎ፣ ፓፓያ፣ አፕል እና ቡና ያሉ ፍሬያማ ተክሎችን በስፋት አካትቷል።
ይህ ስትራቴጂያዊ እርምጃ ፕሮጀክቱን ከአካባቢ ጥበቃ ባለፈ የቤተሰብ የምግብ ዋስትናን የሚያረጋግጥ እና አባወራዎችን የገበያ ተጠቃሚ የሚያደርግ፣ ብሎም የሀገራችን የግብርና ምርት የወጪ ንግድ የሚያሳድግ የኢኮኖሚ ሞተር አድርጎታል።
ይህም የአካባቢ ጥበቃን ከዜጎች የዕለት ተዕለት ኑሮ ማሻሻል ግብ ጋር በማስተሳሰር ዘላቂነቱ የተረጋገጠ የልማት ምሰሶ እንዲሆን አስችሎታል።
3. የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ግንባታ እና የወጣቶች የሥራ ዕድል ፈጠራ
በመላ ሀገራችን የተቋቋሙት በዐሥር ሺዎች የሚቆጠሩ የችግኝ ማፍያ ጣቢያዎች ለብዙ ዜጎች፣ በተለይም ለወጣቶች እና ለሴቶች አዲስ እና ዘላቂ የገቢ ምንጭ ሆነዋል።
ችግኝ ማፍላት፣ መንከባከብ እና ለገበያ ማቅረብ በራሱ አዲስ የኢንቨስትመንት ዘርፍ እና የሥራ ዕድል በመፍጠር፣ የሀገራችንን የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ጅማሮ በጠንካራ መሠረት ላይ አኑሮታል።
ችግኞች ከተተከሉ በኋላ የሚደረገው ጥበቃ እና ክብካቤም በርካታ ወጣቶችን ተጠቃሚ ያደረገ ቋሚ የሥራ ዘርፍ መሆን ችሏል።
4. የውኃ ሀብት እና የታላላቅ ሀገራዊ የልማት ፕሮጀክቶች ዋስትና
በስፋት የተከናወነው የደን ልማት እና የአፈር ጥበቃ ሥራ የአፈር መሸርሸርን በመቀነስ፣ እንደ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ያሉ ሀገራዊ የሃይድሮ ኤሌክትሪክ ማመንጫዎች በደለል እንዳይሞሉ የመከላከል ታሪካዊ ሚና ተጫውቷል።
በተጨማሪም የከርሰ ምድር ውኃ መጠን እንዲያገግም እና የደረቁ የምንጭ ውኃዎች መልሰው እንዲፈልቁ በማድረግ አስተማማኝ የውኃ ዋስትናን እያረጋገጠ ይገኛል።
ይህ ታላላቅ መሠረተ ልማቶችን የመጠበቅ አቅም ለኢትዮጵያ ብልጽግና ብቻ ሳይሆን፣ ሀገራችን የውኃ ምንጭ ለሆነችላቸው የታችኛው ተፋሰስ ሀገራት ጭምር ትልቅ ትሩፋት ነው።
5. አረንጓዴ ዲፕሎማሲ እና የቀጣናዊ ትሥሥር ማጠናከሪያ
ኢትዮጵያ ያዘጋጀቻቸውን ችግኞች እንደ ጂቡቲ፣ ሶማሊያ፣ ደቡብ ሱዳን እና ኬንያ ላሉት ጎረቤት ሀገራት በማጋራት፣ የምሥራቅ አፍሪካን እና የአፍሪካ ቀንድን የቀጣና አየር ንብረት ለውጥ ተግዳሮት በጋራ የመከላከል መሪነት ሚናዋን በተግባር አሳይታለች።
ይህም አረንጓዴ ዐሻራን የድንበር ተሻጋሪ ዲፕሎማሲ፣ የቀጠናው ሰላም እና የጋራ ልማት መሣሪያ አድርጎታል።
በርካታ የአፍሪካ ሀገራትም የኢትዮጵያን ፈለግ በመከተል የአረንጓዴ ልማትን በሀገሮቻቸው እያስፋፉ ይገኛሉ።
ከዚህ ባሻገር፣ ኢትዮጵያ ባመጣቻቸው ተጨባጭ ስኬቶች “ዘላቂ የደን ልማት አያያዝ እና አጠቃቀም” በሚል ዘርፍ ከዓለም የምግብ እና እርሻ ድርጅት (FAO) ከፍተኛ እውቅናን አግኝታለች።
6. የከተሞች ሥነ-ምኅዳር መታደስ እና የኮሪደር ልማት ውበት
አረንጓዴ ዐሻራ በገጠር ተራራዎች ብቻ ተወስኖ ሳይቀር ወደ ከተሞች በመግባት የዘመናዊ ፓርኮች ግንባታ፣ የከተማ አረንጓዴ ልማት እና አሁን ላይ በስፋት እየተተገበረ ላለው የኮሪደር ልማት ዋነኛ አካል ሆኗል።
ይህም የከተሞችን የአየር ጥራት በከፍተኛ ደረጃ ከመጨመሩም በላይ፣ የሥነ-ሕይወት ስብጥርን ወደ ነበረበት በመመለስ እና ለዜጎች ምቹ የመዝናኛ እና የኑሮ አካባቢን በመፍጠር የከተሞቻችንን ገጽታ ሙሉ በሙሉ በመለወጥ ላይ ይገኛል።
7. ሕዝባዊ ንቅናቄ እና የዜግነት አገልግሎት ባህል ግንባታ
በአንድ ጀምበር በመቶ ሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎች በነቂስ ወጥተው ችግኝ የመተከል ልምዳቸው፣ የአካባቢ ጥበቃን ከዘመቻነት አውጥቶ የባህል እና የዜግነት ግዴታ አካል አድርጎታል።
ይህም የሕዝባዊ ወንድማማችነትን ያጠናከረ እና የአካባቢ ጥበቃ ግንዛቤን በማሳደግ ለቀጣዩ ትውልድ የሚሻገር እጅግ ግዙፍ ማኅበራዊ እና ሥነ-ልቦናዊ ስኬት ነው።
በአጠቃላይ አረንጓዴ ዐሻራ ባለፉት ሰባት ዓመታት የተፈጥሮ ሀብታችንን ከመመለስ አልፎ ሀገራዊ አንድነትን ያጠናከረ፣ የማክሮ ኢኮኖሚ አቅማችንን የገነባ እና ኢትዮጵያን በዓለም አቀፍ መድረክ ለአየር ንብረት ለውጥ መፍትሔ አቅራቢ ሀገር ያደረገ አንጸባራቂ አዲስ የታሪክ ምዕራፍ ነው።
በለሚ ታደሰ
#ethiopia #ebc #greenlegacy #climateaction #greendiplomacy #greeneconomy
*************
አረንጓዴ ዐሻራ በኢትዮጵያ ምድር ከተጀመረበት ጊዜ አንስቶ ባለፉት ሰባት ዓመታት፣ ሀገራችንን ከአፈር መሸርሸር እና ከበረሃማነት የመታደግ ሀገራዊ ራዕይ ብቻ ሳይሆን፤ የምድርን ሕይወት የሚያድስ፣ የዜጎችን ሥነ-ልቦናዊ አስተሳሰብ የሚቀርጽ እና ኢኮኖሚያዊ አቅም የሚገነባ ታላቅ ሕዝባዊ ንቅናቄ ሆኖ ዘልቋል።
ይህ ሀገራዊ የሕልውና ጥረት ከሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ ስትራቴጂዎች ጋር ተናብቦ ባለፉት ሰባት ዓመታት ያስመዘገባቸው ሰባት ዋና ዋና ተጨባጭ ስኬቶች እንደሚከተለው ተተንትነዋል።
1. የችግኝ ብዛትን ከጽድቀት ምጣኔ ጋር ያጣመረ አዲስ ታሪካዊ ሽግግር
ባለፉት ሰባት ዓመታት በቢሊዮኖች የሚቆጠሩ ችግኞች መተከላቸው ብቻ ሳይሆን፣ የተከላው ዋና ትኩረት ወደ ጥራት እና ድኅረ-ተከላ እንክብካቤ በማደጉ የችግኞች ጽድቀት ምጣኔ ከ80 በመቶ በላይ ማደግ ችሏል።
ይህም ቀደም ሲል የነበረውን "መተከል እንጂ አለመጽደቅ" የሚል የብክነት ታሪክን በመቀየር በቆላ እና በደጋ አካባቢዎች የተጎዱ መሬቶች በፍጥነት አረንጓዴ እንዲለብሱ እና ሥነ-ምኅዳራዊ ሚዛን እንዲጠበቅ አድርጓል።
2. ከአካባቢ ጥበቃ ወደ የምግብ ዋስትና የተደረገ መዋቅራዊ የኢኮኖሚ ሽግግር
አረንጓዴ ዐሻራ ከተፈጥሮ የደን ዛፎች ባሻገር እንደ አቮካዶ፣ ማንጎ፣ ፓፓያ፣ አፕል እና ቡና ያሉ ፍሬያማ ተክሎችን በስፋት አካትቷል።
ይህ ስትራቴጂያዊ እርምጃ ፕሮጀክቱን ከአካባቢ ጥበቃ ባለፈ የቤተሰብ የምግብ ዋስትናን የሚያረጋግጥ እና አባወራዎችን የገበያ ተጠቃሚ የሚያደርግ፣ ብሎም የሀገራችን የግብርና ምርት የወጪ ንግድ የሚያሳድግ የኢኮኖሚ ሞተር አድርጎታል።
ይህም የአካባቢ ጥበቃን ከዜጎች የዕለት ተዕለት ኑሮ ማሻሻል ግብ ጋር በማስተሳሰር ዘላቂነቱ የተረጋገጠ የልማት ምሰሶ እንዲሆን አስችሎታል።
3. የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ግንባታ እና የወጣቶች የሥራ ዕድል ፈጠራ
በመላ ሀገራችን የተቋቋሙት በዐሥር ሺዎች የሚቆጠሩ የችግኝ ማፍያ ጣቢያዎች ለብዙ ዜጎች፣ በተለይም ለወጣቶች እና ለሴቶች አዲስ እና ዘላቂ የገቢ ምንጭ ሆነዋል።
ችግኝ ማፍላት፣ መንከባከብ እና ለገበያ ማቅረብ በራሱ አዲስ የኢንቨስትመንት ዘርፍ እና የሥራ ዕድል በመፍጠር፣ የሀገራችንን የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ጅማሮ በጠንካራ መሠረት ላይ አኑሮታል።
ችግኞች ከተተከሉ በኋላ የሚደረገው ጥበቃ እና ክብካቤም በርካታ ወጣቶችን ተጠቃሚ ያደረገ ቋሚ የሥራ ዘርፍ መሆን ችሏል።
4. የውኃ ሀብት እና የታላላቅ ሀገራዊ የልማት ፕሮጀክቶች ዋስትና
በስፋት የተከናወነው የደን ልማት እና የአፈር ጥበቃ ሥራ የአፈር መሸርሸርን በመቀነስ፣ እንደ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ያሉ ሀገራዊ የሃይድሮ ኤሌክትሪክ ማመንጫዎች በደለል እንዳይሞሉ የመከላከል ታሪካዊ ሚና ተጫውቷል።
በተጨማሪም የከርሰ ምድር ውኃ መጠን እንዲያገግም እና የደረቁ የምንጭ ውኃዎች መልሰው እንዲፈልቁ በማድረግ አስተማማኝ የውኃ ዋስትናን እያረጋገጠ ይገኛል።
ይህ ታላላቅ መሠረተ ልማቶችን የመጠበቅ አቅም ለኢትዮጵያ ብልጽግና ብቻ ሳይሆን፣ ሀገራችን የውኃ ምንጭ ለሆነችላቸው የታችኛው ተፋሰስ ሀገራት ጭምር ትልቅ ትሩፋት ነው።
5. አረንጓዴ ዲፕሎማሲ እና የቀጣናዊ ትሥሥር ማጠናከሪያ
ኢትዮጵያ ያዘጋጀቻቸውን ችግኞች እንደ ጂቡቲ፣ ሶማሊያ፣ ደቡብ ሱዳን እና ኬንያ ላሉት ጎረቤት ሀገራት በማጋራት፣ የምሥራቅ አፍሪካን እና የአፍሪካ ቀንድን የቀጣና አየር ንብረት ለውጥ ተግዳሮት በጋራ የመከላከል መሪነት ሚናዋን በተግባር አሳይታለች።
ይህም አረንጓዴ ዐሻራን የድንበር ተሻጋሪ ዲፕሎማሲ፣ የቀጠናው ሰላም እና የጋራ ልማት መሣሪያ አድርጎታል።
በርካታ የአፍሪካ ሀገራትም የኢትዮጵያን ፈለግ በመከተል የአረንጓዴ ልማትን በሀገሮቻቸው እያስፋፉ ይገኛሉ።
ከዚህ ባሻገር፣ ኢትዮጵያ ባመጣቻቸው ተጨባጭ ስኬቶች “ዘላቂ የደን ልማት አያያዝ እና አጠቃቀም” በሚል ዘርፍ ከዓለም የምግብ እና እርሻ ድርጅት (FAO) ከፍተኛ እውቅናን አግኝታለች።
6. የከተሞች ሥነ-ምኅዳር መታደስ እና የኮሪደር ልማት ውበት
አረንጓዴ ዐሻራ በገጠር ተራራዎች ብቻ ተወስኖ ሳይቀር ወደ ከተሞች በመግባት የዘመናዊ ፓርኮች ግንባታ፣ የከተማ አረንጓዴ ልማት እና አሁን ላይ በስፋት እየተተገበረ ላለው የኮሪደር ልማት ዋነኛ አካል ሆኗል።
ይህም የከተሞችን የአየር ጥራት በከፍተኛ ደረጃ ከመጨመሩም በላይ፣ የሥነ-ሕይወት ስብጥርን ወደ ነበረበት በመመለስ እና ለዜጎች ምቹ የመዝናኛ እና የኑሮ አካባቢን በመፍጠር የከተሞቻችንን ገጽታ ሙሉ በሙሉ በመለወጥ ላይ ይገኛል።
7. ሕዝባዊ ንቅናቄ እና የዜግነት አገልግሎት ባህል ግንባታ
በአንድ ጀምበር በመቶ ሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎች በነቂስ ወጥተው ችግኝ የመተከል ልምዳቸው፣ የአካባቢ ጥበቃን ከዘመቻነት አውጥቶ የባህል እና የዜግነት ግዴታ አካል አድርጎታል።
ይህም የሕዝባዊ ወንድማማችነትን ያጠናከረ እና የአካባቢ ጥበቃ ግንዛቤን በማሳደግ ለቀጣዩ ትውልድ የሚሻገር እጅግ ግዙፍ ማኅበራዊ እና ሥነ-ልቦናዊ ስኬት ነው።
በአጠቃላይ አረንጓዴ ዐሻራ ባለፉት ሰባት ዓመታት የተፈጥሮ ሀብታችንን ከመመለስ አልፎ ሀገራዊ አንድነትን ያጠናከረ፣ የማክሮ ኢኮኖሚ አቅማችንን የገነባ እና ኢትዮጵያን በዓለም አቀፍ መድረክ ለአየር ንብረት ለውጥ መፍትሔ አቅራቢ ሀገር ያደረገ አንጸባራቂ አዲስ የታሪክ ምዕራፍ ነው።
በለሚ ታደሰ
#ethiopia #ebc #greenlegacy #climateaction #greendiplomacy #greeneconomy
Sponsored by
Surafel
2 days ago
ተራዝሟል!!
የመኖሪያ ቤት አከራይ ተከራይ ውል እድሳት እስከ ነሀሴ 30 /2018 ዓ.ም ድረስ ተራዘመ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የዜጎችን የኑሮ ጫና ለመቀነስ እና በኪራይ ገበያው ላይ የሚስተዋሉ ህገ-ወጥና ዘፈቀዳዊ አሰራሮችን በዘላቂነት ለመግታት እየወሰደ ባለው እርምጃ የቤት ኪራይ ጭማሪ ጣሪያ 11.5% ሆኖ መወስኑን ተከትሎ የውል እድሳት ምዝገባም ከ ሐምሌ 1 / 2018 ዓ.ም ጀምሮ እየተካሄደ መሆኑ ይታወቃል፡፡
ይህንን ተከትሎ በመላው ከተማዋ የሚገኙ የግል መኖሪያ ቤቶች የአከራይ-ተከራይ የውል እድሳት ምዝገባ ግዜ እስከ እስከ ሀምሌ 30 /2018 ዓ.ም የነበረው እስከ ነሀሴ 30 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ መራዘሙን የቤቶች ልማት እና አስተዳደር ቢሮ አሳውቋል።
የውል እድሳት ግዜው በህብረተሰቡ ጥያቄ መስረት የተራዘመ ሲሆን ነዋሪው ያለምንም መጨናነቅ እንዲዋዋል ታሳቢ ያደረገ መሆኑንም ቢሮው ገልጿል።
ህብረተሰቡ በሁሉም ክፍለ ከተማ ቤቶች አስተዳደር ፅ/ቤት ፤ በየወረዳው በተዘጋጁ የውል ቦታዎች እና በሁሉም ክፍለ ከተማ አዲስ መሶብ አስፈላጊውን መረጃ ይዞ በመገኘት አገልግሎቱን ማግኘት የሚቻል መሆኑን ቢሮው በድጋሚ ያሳውቃል፡፡
የአዲስ አበባ ቤቶች ልማት እና አስተዳደር ቢሮ
የመኖሪያ ቤት አከራይ ተከራይ ውል እድሳት እስከ ነሀሴ 30 /2018 ዓ.ም ድረስ ተራዘመ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የዜጎችን የኑሮ ጫና ለመቀነስ እና በኪራይ ገበያው ላይ የሚስተዋሉ ህገ-ወጥና ዘፈቀዳዊ አሰራሮችን በዘላቂነት ለመግታት እየወሰደ ባለው እርምጃ የቤት ኪራይ ጭማሪ ጣሪያ 11.5% ሆኖ መወስኑን ተከትሎ የውል እድሳት ምዝገባም ከ ሐምሌ 1 / 2018 ዓ.ም ጀምሮ እየተካሄደ መሆኑ ይታወቃል፡፡
ይህንን ተከትሎ በመላው ከተማዋ የሚገኙ የግል መኖሪያ ቤቶች የአከራይ-ተከራይ የውል እድሳት ምዝገባ ግዜ እስከ እስከ ሀምሌ 30 /2018 ዓ.ም የነበረው እስከ ነሀሴ 30 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ መራዘሙን የቤቶች ልማት እና አስተዳደር ቢሮ አሳውቋል።
የውል እድሳት ግዜው በህብረተሰቡ ጥያቄ መስረት የተራዘመ ሲሆን ነዋሪው ያለምንም መጨናነቅ እንዲዋዋል ታሳቢ ያደረገ መሆኑንም ቢሮው ገልጿል።
ህብረተሰቡ በሁሉም ክፍለ ከተማ ቤቶች አስተዳደር ፅ/ቤት ፤ በየወረዳው በተዘጋጁ የውል ቦታዎች እና በሁሉም ክፍለ ከተማ አዲስ መሶብ አስፈላጊውን መረጃ ይዞ በመገኘት አገልግሎቱን ማግኘት የሚቻል መሆኑን ቢሮው በድጋሚ ያሳውቃል፡፡
የአዲስ አበባ ቤቶች ልማት እና አስተዳደር ቢሮ
2 days ago
በጅማ ዞን ለሚካሄደው የአንድ ጀምበር ችግኝ ተከላ የተለያዩ እንግዶች ጅማ ገቡ!
በኦሮሚያ ክልል ጅማ ዞን ሰቃ ወረዳ በቡዬ ቀጨማ ቀበሌ ነገ ሐምሌ 27 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 12፡00 ሰዓት ጀምሮ የሚካሄደውና ለመላው ኢትዮጵያውያን ጥሪ የቀረበበት የአንድ ጀምበር የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር ዝግጅት መጠጠናቀቁ ተገለጸ። በአገር አቀፍ ደረጃ በአንድ ጀምበር ከ800 ሚሊዮን በላይ ችግኞችን ለመትከል በተያዘው ግብ መሠረት የሚከናወነው ይህ መርሃ-ግብር፤ አረንጓዴ አሻራን በማሳረፍ ረገድ የትውልድ ሀላፊነትን ለመወጣት ያለመ እንደሆነ ተነግሯል።
ይህ ሀገር አቀፍ አቅጣጫን መሠረት ያደረገ ታላቅ መርሃ-ግብር በግሪን ዌቭ አሊያንስ ሀገር በቀል ግብረ-ሰናይ ድርጅት፣ ከኢፌድሪ ግብርና ሚኒስቴር እና በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አዘጋጅነት የቀረበ ሲሆን፤ የኢትዮጵያ አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን እና የኦሮሚያ ግብርና ቢሮ አስፈላጊውን ቴክኒካል ድጋፍ በማድረግ ተሳትፏል።።
ለዝግጅቱ ስኬት በጅማ ከተማ የደረሱ ታዋቂ ግለሰቦች፣ አርቲስቶች፣ ጋዜጠኞች፣ ቲክቶክሮች እና የጥሪው ተጋባዦች በዞኑ እና በከተማ አስተዳደሩ፣ በአባ ገዳዎች፣ በሀደ ሲንቄዎች እንዲሁም በሀገር ሽማግሌዎች አቀባበል ተደርጎላቸዋል። ነገ በሚካሄደው በዚህ ታሪካዊ ኹነት ህብረተሰቡ በነቃ ሁኔታ እንዲሳተፍ አዘጋጆቹ ጥሪ አቅርበዋል።
በኦሮሚያ ክልል ጅማ ዞን ሰቃ ወረዳ በቡዬ ቀጨማ ቀበሌ ነገ ሐምሌ 27 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 12፡00 ሰዓት ጀምሮ የሚካሄደውና ለመላው ኢትዮጵያውያን ጥሪ የቀረበበት የአንድ ጀምበር የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር ዝግጅት መጠጠናቀቁ ተገለጸ። በአገር አቀፍ ደረጃ በአንድ ጀምበር ከ800 ሚሊዮን በላይ ችግኞችን ለመትከል በተያዘው ግብ መሠረት የሚከናወነው ይህ መርሃ-ግብር፤ አረንጓዴ አሻራን በማሳረፍ ረገድ የትውልድ ሀላፊነትን ለመወጣት ያለመ እንደሆነ ተነግሯል።
ይህ ሀገር አቀፍ አቅጣጫን መሠረት ያደረገ ታላቅ መርሃ-ግብር በግሪን ዌቭ አሊያንስ ሀገር በቀል ግብረ-ሰናይ ድርጅት፣ ከኢፌድሪ ግብርና ሚኒስቴር እና በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አዘጋጅነት የቀረበ ሲሆን፤ የኢትዮጵያ አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን እና የኦሮሚያ ግብርና ቢሮ አስፈላጊውን ቴክኒካል ድጋፍ በማድረግ ተሳትፏል።።
ለዝግጅቱ ስኬት በጅማ ከተማ የደረሱ ታዋቂ ግለሰቦች፣ አርቲስቶች፣ ጋዜጠኞች፣ ቲክቶክሮች እና የጥሪው ተጋባዦች በዞኑ እና በከተማ አስተዳደሩ፣ በአባ ገዳዎች፣ በሀደ ሲንቄዎች እንዲሁም በሀገር ሽማግሌዎች አቀባበል ተደርጎላቸዋል። ነገ በሚካሄደው በዚህ ታሪካዊ ኹነት ህብረተሰቡ በነቃ ሁኔታ እንዲሳተፍ አዘጋጆቹ ጥሪ አቅርበዋል።
2 days ago
ባህርዳር ዩኒቨርስቲ በEVACONET የአርክቴክቸር ዲዛይን ውድድር አንደኛ ሆነ
#ethiopia | አዲስ አበባ – በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ የተዘጋጀው የEVACONET ዲጂታል የኮንስትራክሽን ገበያ ፕላትፎርም የምረቃ ሥነ ሥርዓት አካል በሆነው የአርክቴክቸር ዲዛይን ውድድር ባህርዳር ዩኒቨርስቲ አንደኛ ደረጃን በማስመዝገብ አሸናፊ ሆኗል።
ውድድሩ በዩኒቨርስቲዎች የአርክቴክቸር ዲፓርትመንት 5ኛ ዓመት ተማሪዎች መካከል የተካሄደ ሲሆን፣ ሀዋሳ ዩኒቨርስቲ ሁለተኛ፣ አዲስ ኮሌጅ ደግሞ ሶስተኛ ደረጃን አግኝተዋል። አዘጋጆቹ ውድድሩ አዳዲስ የፈጠራ ስራዎችን ያስተዋወቀ እንደነበር ገልጸው፣ ከዚህ በኋላም በየዓመቱ እንደሚካሄድ አስታውቀዋል።
EVACONET በኢንጂነር አቤሴሎም መለሰ የተቋቋመ ዲጂታል የኮንስትራክሽን ገበያ ፕላትፎርም ሲሆን፣ የኮንስትራክሽን ማቴሪያል ወቅታዊ ዋጋዎችን በማነጻጸር ሻጮችና ገዢዎችን በአንድ መድረክ የሚያገናኝ የዲጂታል ገበያ ሥርዓት ነው።
በምረቃ ሥነ ሥርዓቱ ላይ የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር ዴኤታ ዶ/ር የትምጌታ አስራት፣ የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ባለስልጣን ኃላፊዎች፣ የዘርፉ ባለድርሻ አካላትና ሌሎች እንግዶች ተገኝተዋል። ተናጋሪዎቹም ፕላትፎርሙ የ"ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030" ራዕይን ለማሳካት እንደሚያግዝ፣ በኮንስትራክሽን ገበያ ውስጥ ግልጽነትና ተወዳዳሪነትን እንደሚያሳድግ ገልጸዋል።
በእለቱ "ሕይወትን በኮንስትራክሽን እንገንባ" በሚል መሪ ቃል የተዘጋጀ የኮንስትራክሽን ፋሽን ሾውና የሞዴሎች ትዕይንትም ቀርቦ የተሳታፊዎችን ቀልብ ስቧል።
ዝግጅቱ ለተሳካ አፈጻጸም አስተዋጽኦ ላደረጉ ተቋማትና ግለሰቦች የእውቅና እና የልዩ ሽልማት ስጦታዎች በመበርከት ተጠናቋል።
#ethiopia | አዲስ አበባ – በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ የተዘጋጀው የEVACONET ዲጂታል የኮንስትራክሽን ገበያ ፕላትፎርም የምረቃ ሥነ ሥርዓት አካል በሆነው የአርክቴክቸር ዲዛይን ውድድር ባህርዳር ዩኒቨርስቲ አንደኛ ደረጃን በማስመዝገብ አሸናፊ ሆኗል።
ውድድሩ በዩኒቨርስቲዎች የአርክቴክቸር ዲፓርትመንት 5ኛ ዓመት ተማሪዎች መካከል የተካሄደ ሲሆን፣ ሀዋሳ ዩኒቨርስቲ ሁለተኛ፣ አዲስ ኮሌጅ ደግሞ ሶስተኛ ደረጃን አግኝተዋል። አዘጋጆቹ ውድድሩ አዳዲስ የፈጠራ ስራዎችን ያስተዋወቀ እንደነበር ገልጸው፣ ከዚህ በኋላም በየዓመቱ እንደሚካሄድ አስታውቀዋል።
EVACONET በኢንጂነር አቤሴሎም መለሰ የተቋቋመ ዲጂታል የኮንስትራክሽን ገበያ ፕላትፎርም ሲሆን፣ የኮንስትራክሽን ማቴሪያል ወቅታዊ ዋጋዎችን በማነጻጸር ሻጮችና ገዢዎችን በአንድ መድረክ የሚያገናኝ የዲጂታል ገበያ ሥርዓት ነው።
በምረቃ ሥነ ሥርዓቱ ላይ የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር ዴኤታ ዶ/ር የትምጌታ አስራት፣ የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ባለስልጣን ኃላፊዎች፣ የዘርፉ ባለድርሻ አካላትና ሌሎች እንግዶች ተገኝተዋል። ተናጋሪዎቹም ፕላትፎርሙ የ"ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030" ራዕይን ለማሳካት እንደሚያግዝ፣ በኮንስትራክሽን ገበያ ውስጥ ግልጽነትና ተወዳዳሪነትን እንደሚያሳድግ ገልጸዋል።
በእለቱ "ሕይወትን በኮንስትራክሽን እንገንባ" በሚል መሪ ቃል የተዘጋጀ የኮንስትራክሽን ፋሽን ሾውና የሞዴሎች ትዕይንትም ቀርቦ የተሳታፊዎችን ቀልብ ስቧል።
ዝግጅቱ ለተሳካ አፈጻጸም አስተዋጽኦ ላደረጉ ተቋማትና ግለሰቦች የእውቅና እና የልዩ ሽልማት ስጦታዎች በመበርከት ተጠናቋል።
2 days ago
በሚቀጥሉት 5 ዓመታት ለትምህርት ጥራት እና ውጤታማነት መጠናከር ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል - የትምህርት ሚኒስቴር
**************************
7ኛው የትምህርት ዘርፍ ልማት ፕሮግራም (ESDP VII) ረቂቅ ዕቅድ ላይ ውይይት ማድረጉን የትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ።
በአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ የምክክር መድረክ ላይ በስትራቴጂያዊ ጉዳዮች የቀረበው 7ኛው የትምህርት ዘርፍ ልማት ፕሮግራም (ESDP VII 2026/27 to 2030/31) ረቂቅ ዕቅድ፣ በሚቀጥሉት አምስት ዓመታት የትምህርት ጥራትና ውጤታማነትን ማጠናከር ዋና ትኩረት እንደሚሆን አመላክቷል።
በረቂቅ ዕቅዱ መሠረት፣ የትምህርት ጥራትን እና ተገቢነትን ለማረጋገጥ ቀደም ሲል የተጀመሩ ሥራዎችን በአዳዲስ አሠራሮች ማጠናከር፣ የትምህርትን ውጤት በተጨባጭ መለካት እና በትምህርት ዘርፍ የቴክኖሎጂ አጠቃቀምን ማሳደግ ቅድሚያ የተሰጣቸው ጉዳዮች መሆናቸው ተገልጿል።
ፕሮግራሙ አዲሱን ሥርዓተ ትምህርት በውጤታማነት መተግበር፣ ምዘናን በብቃት ላይ የተመሠረተ እንዲሆን ማድረግ፣ የተማሪዎችን የመማር ውጤት ማሻሻል እንዲሁም በቋንቋ፣ በሒሳብ እና በሳይንስ ትምህርቶች ያላቸውን ብቃት ማሳደግን እንደ ዋና ተግባራት አካቷል።
በተጨማሪም የዲጂታል ትምህርትን ማስፋፋት፣ የብሔራዊ ፈተናዎችን ማዘመን፣ በቴክኒክ እና ሙያ ሥልጠና (TVET) እና በከፍተኛ ትምህርት መካከል ያለውን ቅንጅት ማጠናከር፣ የመምህራንን ሙያዊ ብቃት እና ማበረታቻ ማሻሻል፣ እንዲሁም የመምህራን ማሠልጠኛ ኮሌጆችን እና ዩኒቨርሲቲዎችን ማጠናከር በዕቅዱ ውስጥ ተካትተዋል።
ረቂቅ ዕቅዱ የትምህርት ጥራት፣ ተገቢነትን ተደራሽነትን እና ፍትሐዊነትን ማረጋገጥ፣ በተፈጥሮ እና በሰው ሠራሽ አደጋዎች ምክንያት የተጎዱ የትምህርት ማኅበረሰቦችን መልሶ ማቋቋም፣ ትምህርትን ሳይቋረጥ እንዲዘልቅ የሚያስችል ሥርዓት መገንባት፣ እንዲሁም ልዩ ፍላጎት ያላቸውን ተማሪዎች እና የሴት ተማሪዎችን የትምህርት ተሳትፎ እና ውጤታማነት ማረጋገጥ ላይም ልዩ ትኩረት መስጠቱን ያመለክታል።
7ኛው የትምህርት ዘርፍ ልማት ፕሮግራም (ESDP VII) ረቂቅ ዕቅድ በምክክር መድረኩ ላይ ቀርቦ፣ በክልል እና በከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊዎች፣ እንዲሁም በዘርፉ ባለድርሻ አካላት ሰፊ ውይይት የተደረገበት መሆኑን ከትምህርት ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።
#ethiopia #ebc #education #ministryofeducation #educationquality
**************************
7ኛው የትምህርት ዘርፍ ልማት ፕሮግራም (ESDP VII) ረቂቅ ዕቅድ ላይ ውይይት ማድረጉን የትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ።
በአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ የምክክር መድረክ ላይ በስትራቴጂያዊ ጉዳዮች የቀረበው 7ኛው የትምህርት ዘርፍ ልማት ፕሮግራም (ESDP VII 2026/27 to 2030/31) ረቂቅ ዕቅድ፣ በሚቀጥሉት አምስት ዓመታት የትምህርት ጥራትና ውጤታማነትን ማጠናከር ዋና ትኩረት እንደሚሆን አመላክቷል።
በረቂቅ ዕቅዱ መሠረት፣ የትምህርት ጥራትን እና ተገቢነትን ለማረጋገጥ ቀደም ሲል የተጀመሩ ሥራዎችን በአዳዲስ አሠራሮች ማጠናከር፣ የትምህርትን ውጤት በተጨባጭ መለካት እና በትምህርት ዘርፍ የቴክኖሎጂ አጠቃቀምን ማሳደግ ቅድሚያ የተሰጣቸው ጉዳዮች መሆናቸው ተገልጿል።
ፕሮግራሙ አዲሱን ሥርዓተ ትምህርት በውጤታማነት መተግበር፣ ምዘናን በብቃት ላይ የተመሠረተ እንዲሆን ማድረግ፣ የተማሪዎችን የመማር ውጤት ማሻሻል እንዲሁም በቋንቋ፣ በሒሳብ እና በሳይንስ ትምህርቶች ያላቸውን ብቃት ማሳደግን እንደ ዋና ተግባራት አካቷል።
በተጨማሪም የዲጂታል ትምህርትን ማስፋፋት፣ የብሔራዊ ፈተናዎችን ማዘመን፣ በቴክኒክ እና ሙያ ሥልጠና (TVET) እና በከፍተኛ ትምህርት መካከል ያለውን ቅንጅት ማጠናከር፣ የመምህራንን ሙያዊ ብቃት እና ማበረታቻ ማሻሻል፣ እንዲሁም የመምህራን ማሠልጠኛ ኮሌጆችን እና ዩኒቨርሲቲዎችን ማጠናከር በዕቅዱ ውስጥ ተካትተዋል።
ረቂቅ ዕቅዱ የትምህርት ጥራት፣ ተገቢነትን ተደራሽነትን እና ፍትሐዊነትን ማረጋገጥ፣ በተፈጥሮ እና በሰው ሠራሽ አደጋዎች ምክንያት የተጎዱ የትምህርት ማኅበረሰቦችን መልሶ ማቋቋም፣ ትምህርትን ሳይቋረጥ እንዲዘልቅ የሚያስችል ሥርዓት መገንባት፣ እንዲሁም ልዩ ፍላጎት ያላቸውን ተማሪዎች እና የሴት ተማሪዎችን የትምህርት ተሳትፎ እና ውጤታማነት ማረጋገጥ ላይም ልዩ ትኩረት መስጠቱን ያመለክታል።
7ኛው የትምህርት ዘርፍ ልማት ፕሮግራም (ESDP VII) ረቂቅ ዕቅድ በምክክር መድረኩ ላይ ቀርቦ፣ በክልል እና በከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊዎች፣ እንዲሁም በዘርፉ ባለድርሻ አካላት ሰፊ ውይይት የተደረገበት መሆኑን ከትምህርት ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።
#ethiopia #ebc #education #ministryofeducation #educationquality
2 days ago
በፔሩ የቱሪስት አውሮፕላን ተከስክሶ 13 ሰዎች ሞቱ
ፔሩ ውስጥ ቱሪስቶችን ጭኖ ሲበርር የነበረ አነስተኛ አውሮፕላን ተከስክሶ፣ በውስጡ የነበሩት 13 ሰዎች በሙሉ ሕይወታቸው ማለፉን የአገሪቱ ባለሥልጣናት እና መገናኛ ብዙኃን ገለጹ።
‘ሴስና ካራቫን ሲ-208’ የተባለው አውሮፕላን ቅዳሜ ዕለት የተከሰከሰው ‘ናዝካ ላይንስ’ በተሰኘው አርኪኦሎጂ ስፍራ በኩል እየበረረ በነበረበት ወቅት ነው። አውሮፕላኑ 11 ተሳፋሪዎች እና ሁለት ፓይለቶች ይዞ ነበር።
ከተሳፋሪዎቹ መካከል ሁለት ጀርመናውያን፣ ሁለት የስፔን ዜጎች እና ሰባት ጣሊያናውያን ቱሪስቶች እንደነበሩ የፔሩ የመንግሥት የዜና ወኪል ዘግቧል። አደጋው የደረሰበት ምክንያት እስካሁን አልታወቀም።
በደቡባዊ ፔሩ የሚገኘው ‘ናዝካ ላይንስ’፣ በበረሃ አሸዋ ላይ የተሳሉ ጥንታዊ የእንስሳት ስዕሎች የሚታዩበት እና በዩኔስኮ የዓለም ቅርስነት የተመዘገበ ታዋቂ የቱሪስት ስፍራ መስህብ ነው።
ብዙውን ጊዜ ቱሪስቶች ስዕሎቹ ምን ያህል ስፋት ያለው ስፍራ ላይ እንዳረፉ ለመመልከት በአነስተኛ አውሮፕላኖች ይበራሉ
የፔሩ ፖሊስ አመራሩ ሜጀር ጆርጅ አንደራዴ "ከአደጋው አስከፊነት የተነሳ በሕይወት የተረፈ ሰው የለም። እስካሁን የአራት ሰዎችን አስከሬን አግኝተናል" ማለታቸውን ኤኤፍፒ ዘግቧል።
‘ፒስኮ’ በተባለው የፔሩ ከተማ ከሚገኝ አየር ማረፊያ የተነሳው አውሮፕላን የተከሰከሰው ፑዌብሎ ቪየሆ የተባለው ክልል ውስጥ ነው።
የዜና ወኪሉ ሮይተርስ ባወጣው አንድ ቪዲዮ ላይ የእሳት አደጋ ሠራተኞች ከስብርባሪዎች ጭስ የሚወጣበት የአደጋ ስፍራ ላይ ውሃ ሲረጩ ያሳያል።
‘ዴ ናስካ’ ግዛት አስተዳደር ባወጣው መግለጫ አውሮፕላኑ ‘ኤሮዲያና’ የተሰኘው የፔሩ የአገር ውስጥ አየር መንገድ ንብረት መሆኑን አስታውቋል።
አየር መንገዱ በበኩሉ ጉዳዩ "የሚመለከታቸው ባለሥልጣናት ከሚያወጧቸው መመሪያዎች ጋር በተጣጣመ መልኩ የበረራ መርሃ ግብሩን እንደሚገመግም" መግለጹን ሮይተርስ ዘግቧል።
ይህ ታዋቂ የቱሪስት መስህብ ባለፉት አስርት ዓመት ውስጥ ሌሎች የአውሮፕላን አደጋዎችንም አስተናግዷል።
በአውሮፓውያኑ 2022 አንድ አነስተኛ የቱሪስት አውሮፕላን በናዝካ ላይስ በኩል ሲበርር ተከስክሶ ሰባት ተሳፋሪዎች ሞተዋል።
2010 ላይ ደግሞ ሌላ የቱሪስት አውሮፕላን ወድቆ ተሳፍረው የነበሩ ስድስት ሰዎችን ገድሏል።
BBC
ፔሩ ውስጥ ቱሪስቶችን ጭኖ ሲበርር የነበረ አነስተኛ አውሮፕላን ተከስክሶ፣ በውስጡ የነበሩት 13 ሰዎች በሙሉ ሕይወታቸው ማለፉን የአገሪቱ ባለሥልጣናት እና መገናኛ ብዙኃን ገለጹ።
‘ሴስና ካራቫን ሲ-208’ የተባለው አውሮፕላን ቅዳሜ ዕለት የተከሰከሰው ‘ናዝካ ላይንስ’ በተሰኘው አርኪኦሎጂ ስፍራ በኩል እየበረረ በነበረበት ወቅት ነው። አውሮፕላኑ 11 ተሳፋሪዎች እና ሁለት ፓይለቶች ይዞ ነበር።
ከተሳፋሪዎቹ መካከል ሁለት ጀርመናውያን፣ ሁለት የስፔን ዜጎች እና ሰባት ጣሊያናውያን ቱሪስቶች እንደነበሩ የፔሩ የመንግሥት የዜና ወኪል ዘግቧል። አደጋው የደረሰበት ምክንያት እስካሁን አልታወቀም።
በደቡባዊ ፔሩ የሚገኘው ‘ናዝካ ላይንስ’፣ በበረሃ አሸዋ ላይ የተሳሉ ጥንታዊ የእንስሳት ስዕሎች የሚታዩበት እና በዩኔስኮ የዓለም ቅርስነት የተመዘገበ ታዋቂ የቱሪስት ስፍራ መስህብ ነው።
ብዙውን ጊዜ ቱሪስቶች ስዕሎቹ ምን ያህል ስፋት ያለው ስፍራ ላይ እንዳረፉ ለመመልከት በአነስተኛ አውሮፕላኖች ይበራሉ
የፔሩ ፖሊስ አመራሩ ሜጀር ጆርጅ አንደራዴ "ከአደጋው አስከፊነት የተነሳ በሕይወት የተረፈ ሰው የለም። እስካሁን የአራት ሰዎችን አስከሬን አግኝተናል" ማለታቸውን ኤኤፍፒ ዘግቧል።
‘ፒስኮ’ በተባለው የፔሩ ከተማ ከሚገኝ አየር ማረፊያ የተነሳው አውሮፕላን የተከሰከሰው ፑዌብሎ ቪየሆ የተባለው ክልል ውስጥ ነው።
የዜና ወኪሉ ሮይተርስ ባወጣው አንድ ቪዲዮ ላይ የእሳት አደጋ ሠራተኞች ከስብርባሪዎች ጭስ የሚወጣበት የአደጋ ስፍራ ላይ ውሃ ሲረጩ ያሳያል።
‘ዴ ናስካ’ ግዛት አስተዳደር ባወጣው መግለጫ አውሮፕላኑ ‘ኤሮዲያና’ የተሰኘው የፔሩ የአገር ውስጥ አየር መንገድ ንብረት መሆኑን አስታውቋል።
አየር መንገዱ በበኩሉ ጉዳዩ "የሚመለከታቸው ባለሥልጣናት ከሚያወጧቸው መመሪያዎች ጋር በተጣጣመ መልኩ የበረራ መርሃ ግብሩን እንደሚገመግም" መግለጹን ሮይተርስ ዘግቧል።
ይህ ታዋቂ የቱሪስት መስህብ ባለፉት አስርት ዓመት ውስጥ ሌሎች የአውሮፕላን አደጋዎችንም አስተናግዷል።
በአውሮፓውያኑ 2022 አንድ አነስተኛ የቱሪስት አውሮፕላን በናዝካ ላይስ በኩል ሲበርር ተከስክሶ ሰባት ተሳፋሪዎች ሞተዋል።
2010 ላይ ደግሞ ሌላ የቱሪስት አውሮፕላን ወድቆ ተሳፍረው የነበሩ ስድስት ሰዎችን ገድሏል።
BBC
Comments