20 days ago
የኢዜማ የድጋፍ መግለጫ
***
ለሰላም የቀረበውን ጥሪ አስመልክቶ ከኢዜማ የተሠጠ የድጋፍ መግለጫ!!
በ 8 ፓርቲዎችና 11 ሲቪክ ማሕበራት የተቋቋመው የትግራይ ሰላምና ለውጥ ፈላጊዎች እንቅስቃሴ ሕጋዊ አካልነቱን ባጣው ሕወሓት አማካኝነት በትግራይ ህዝብ ላይ እየተደረገ ያለው አፈና፣ ስቃይ እና እንግልት እንዲቆም እና ጦርነት እንዲቀር ጫና ለማድረግ ያለመ የሰላማዊ ሰልፍ በአዲስ አበባ እንደጠራ መረጃ ደርሶናል፤ የለውጥ እንቅስቃሴው ሁሉም ይህን ሰላማዊ ዓላማ የሚደግፉ ኢትዮጵያውያን በሰልፉ ድጋፋቸውን እንዲሰጡም ጥሪ አቅርቧል።
ፓርቲያችን ኢዜማ የትግራይን ህዝብ ከዳግም ጦርነት እና ስቃይ ለማዳን የሚደረጉ ሰላማዊ እንቅስቃሴዎች ሁሉ እንደሚደግፍ በተደጋጋሚ በገለፀው መሠረት ለዚህ ሰላማዊ ሰልፍ ይፋዊ ድጋፉን እየገለፀ የኢዜማ አባላትና ደጋፊዎችም በሰልፉ በመገኘት እምቢ ለጦርነት የሚል ድጋፋቸውን እንዲያሳዩ ጥሪውን ያቀርባል።
እምቢ ለጦርነት!
የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ (ኢዜማ)
***
ለሰላም የቀረበውን ጥሪ አስመልክቶ ከኢዜማ የተሠጠ የድጋፍ መግለጫ!!
በ 8 ፓርቲዎችና 11 ሲቪክ ማሕበራት የተቋቋመው የትግራይ ሰላምና ለውጥ ፈላጊዎች እንቅስቃሴ ሕጋዊ አካልነቱን ባጣው ሕወሓት አማካኝነት በትግራይ ህዝብ ላይ እየተደረገ ያለው አፈና፣ ስቃይ እና እንግልት እንዲቆም እና ጦርነት እንዲቀር ጫና ለማድረግ ያለመ የሰላማዊ ሰልፍ በአዲስ አበባ እንደጠራ መረጃ ደርሶናል፤ የለውጥ እንቅስቃሴው ሁሉም ይህን ሰላማዊ ዓላማ የሚደግፉ ኢትዮጵያውያን በሰልፉ ድጋፋቸውን እንዲሰጡም ጥሪ አቅርቧል።
ፓርቲያችን ኢዜማ የትግራይን ህዝብ ከዳግም ጦርነት እና ስቃይ ለማዳን የሚደረጉ ሰላማዊ እንቅስቃሴዎች ሁሉ እንደሚደግፍ በተደጋጋሚ በገለፀው መሠረት ለዚህ ሰላማዊ ሰልፍ ይፋዊ ድጋፉን እየገለፀ የኢዜማ አባላትና ደጋፊዎችም በሰልፉ በመገኘት እምቢ ለጦርነት የሚል ድጋፋቸውን እንዲያሳዩ ጥሪውን ያቀርባል።
እምቢ ለጦርነት!
የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ (ኢዜማ)
22 days ago
በምርጫ አሸንፈው ምክር ቤት ከገቡ ተፎካካሪ ፓርቲዎች ጋር በጋራ የመስራት ዓላማ ያለው "ኮከስ" ለመመስረት ማቀዱን ኢዜማ አስታወቀ
የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ (ኢዜማ) በ2019 ዓ.ም. ሥራ በሚጀምረው የኢፌዲሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፣ ከሌሎች ተፎካካሪ ፓርቲዎች ጋር በጋራ ለመስራት የሚያስችለውን "ኮከስ" በመመስረት የመሥራት እቅድ እንዳለው አስታውቋል።
ፓርቲው እንደ አብን ካሉ ምክር ቤት ለመግባት የሚያስችላቸውን ድምጽ ካገኙ የፖለቲካ ኃይሎች ጋር በመቀናጀት በሚያስማሙ የመታገያ አጀንዳዎች ላይ ለመስራት እንዳቀደ ገልጿል።
የኢዜማ የስራ አስፈጻሚ አባል አርክቴክት ዮሐንስ መኮንን እንደገለጹት፤ ፓርላማ በገቡ ተፎካካሪ ፓርቲዎች የሚመሰረተው ኮከስ አላማ በምክር ቤቱ የጋራ አጀንዳዎችን በማቅረብ ተጽዕኖ መፍጠር ነው።
ጥምረቱ ለሕዝብ የሚጠቅሙ ጉዳዮች በገዢው ፓርቲ ተቀባይነት እንዲያገኙ ከፍ ያለ አስተዋጽኦ ይኖረዋል። ለዚህ ተግባራዊነትም ፓርቲው ከአንዳንድ የፖለቲካ ድርጅቶች ጋር የመጀመሪያ ደረጃ ምክክር ጀምሯል ተብሏል።)አርክቴክት ዮሐንስ እንዳብራሩት፤ ጥምረቱ በዋናነት በሕዝብ ጥቅም ላይ ያተኮሩ ጉዳዮችን ለመደገፍ የታለመ ነው።
ፓርቲው የሀገርን ሉዓላዊነት ማስጠበቅና የብሔርተኝነት እሳቤን መታገል እንደ ዋና ግቡ ማስቀመጡን እና ህዝብን በሚጠቅሙ የጋራ ፍላጎቶች ላይ ግን ከሌሎች ተፎካካሪ ፓርቲዎች ጋር አብሮ ለመሥራት ዝግጁ መሆኑን አመልክተዋል።
ይህ የትብብር ስልት በምክር ቤቱ ውስጥ ለሚደረጉ ውይይቶች ሚዛን ይፈጥራል ብለው እንደሚያምኑ አርክቴክቱ ገልጸዋል
#አሐዱ
የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ (ኢዜማ) በ2019 ዓ.ም. ሥራ በሚጀምረው የኢፌዲሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፣ ከሌሎች ተፎካካሪ ፓርቲዎች ጋር በጋራ ለመስራት የሚያስችለውን "ኮከስ" በመመስረት የመሥራት እቅድ እንዳለው አስታውቋል።
ፓርቲው እንደ አብን ካሉ ምክር ቤት ለመግባት የሚያስችላቸውን ድምጽ ካገኙ የፖለቲካ ኃይሎች ጋር በመቀናጀት በሚያስማሙ የመታገያ አጀንዳዎች ላይ ለመስራት እንዳቀደ ገልጿል።
የኢዜማ የስራ አስፈጻሚ አባል አርክቴክት ዮሐንስ መኮንን እንደገለጹት፤ ፓርላማ በገቡ ተፎካካሪ ፓርቲዎች የሚመሰረተው ኮከስ አላማ በምክር ቤቱ የጋራ አጀንዳዎችን በማቅረብ ተጽዕኖ መፍጠር ነው።
ጥምረቱ ለሕዝብ የሚጠቅሙ ጉዳዮች በገዢው ፓርቲ ተቀባይነት እንዲያገኙ ከፍ ያለ አስተዋጽኦ ይኖረዋል። ለዚህ ተግባራዊነትም ፓርቲው ከአንዳንድ የፖለቲካ ድርጅቶች ጋር የመጀመሪያ ደረጃ ምክክር ጀምሯል ተብሏል።)አርክቴክት ዮሐንስ እንዳብራሩት፤ ጥምረቱ በዋናነት በሕዝብ ጥቅም ላይ ያተኮሩ ጉዳዮችን ለመደገፍ የታለመ ነው።
ፓርቲው የሀገርን ሉዓላዊነት ማስጠበቅና የብሔርተኝነት እሳቤን መታገል እንደ ዋና ግቡ ማስቀመጡን እና ህዝብን በሚጠቅሙ የጋራ ፍላጎቶች ላይ ግን ከሌሎች ተፎካካሪ ፓርቲዎች ጋር አብሮ ለመሥራት ዝግጁ መሆኑን አመልክተዋል።
ይህ የትብብር ስልት በምክር ቤቱ ውስጥ ለሚደረጉ ውይይቶች ሚዛን ይፈጥራል ብለው እንደሚያምኑ አርክቴክቱ ገልጸዋል
#አሐዱ
30 days ago
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በፖለቲካ ዙሪያ ያነሷቸው ዋና ዋና ሀሳቦች፡-
**********************
👉🏽ላለፉት አምስት ዓመታት በምክር ቤቱ ውስጥ የሕዝብን እና የፓርቲያቸውን ድምጽ ሲያሰሙ ለነበሩ የተፎካካሪ ፓርቲ አባላት (እንደ ኢዜማ፣ አብን እና ሌሎችም) እንዲሁም ለብልጽግና አባላት ከፍተኛ ምስጋና አቅርበዋል።
👉🏽በዘንድሮው ምርጫ ምክንያት ወደ ምክር ቤት ለማይመለሱ የተፎካካሪ ፓርቲ አባላት፣ የመንግሥት ፍላጎት በጋራ መሥራት መሆኑን በመግለጽ፤ ከምክር ቤት ውጭም ቢሆን ሀገርን ለማልማት ከመንግሥት ጋር አብረው እንዲሠሩ ጥሪ አቅርበዋል።
👉🏽የዘንድሮው ምርጫ ከተለመደው የፖለቲካ ፉክክር ባለፈ፣ ራሱ ምርጫው እንዳይካሄድ በ"ባንዳዎች" እና ፀረ-ምርጫ ኃይሎች ከፍተኛ ጫና እና ማሸማቀቅ እንደነበረበት አንስተዋል።
👉🏽ሕዝቡ ማስፈራሪያዎችን ወደጎን በመተው ሌሊት ወጥቶ በመሰለፍ ድምፁን መስጠቱን፤ በዚህም ፅንፈኝነትን፣ ባንዳነትን እና ዘረኝነትን እንደማይፈልግ በአንድ ድምፅ ማሳየቱን ገልጸዋል።
👉🏽ሕዝቡ ለመንግሥት ጅምር ሥራዎች ዕውቅና በመስጠት ድምፁን ቢሰጥም፣ ይህ ድምጽ "ባዶ ቼክ" መሆኑን አሳስበዋል።
👉🏽ሕዝቡ ሥርአታዊ ሌብነት (ሙስና) እንዲጠፋ እና አገልግሎት እንዲሻሻል አደራ መስጠቱን፤ ይህን አደራ መንግሥት በአግባቡ ካልተወጣ፣ ጥይት ሳይፈራ የመረጠው ሕዝብ በተመሳሳይ ድፍረት የተቃውሞ እርምጃ ሊወስድ እንደሚችል አስጠንቅቀዋል።
👉🏽ብልጽግና ፓርቲ ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ ሲል፣ 15 በመቶ የሚሆነውን የምክር ቤት ወንበር ተፎካካሪ ፓርቲዎች ብቻቸውን እንዲወዳደሩበት ማድረጉን እና ይህም በርካታ ፓርቲዎች ፓርላማ እንዲገቡ ዕድል መፍጠሩን አብራርተዋል።
👉🏽በሀገራዊ ምክክሩ ላይ ብልጽግና ፓርቲ ይዞት ከሚቀርባቸው አጀንዳዎች አንዱ፣ በሥልጣን ላይ ያለ መንግሥት (መሪ) ከሁለት የምርጫ ዘመን በላይ መቆየት የለበትም የሚል የሕገ-መንግስት ማሻሻያ ሀሳብ መሆኑን አስታውቀዋል።
👉🏽ጠቅላይ ሚኒስትሩ ራሳቸው ከ225 በላይ፣ ፓርቲው ደግሞ ከ4 ሺህ በላይ የሕዝብ መድረኮችን ማካሄዱን፤ እንዲሁም የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽኑ የሕዝብ ውይይቶችን በስፋት እያደረገ መሆኑን አንስተዋል።
👉🏽ታፍነው የቆዩ ብሶቶች በነጻነት እንዲወጡ በመደረጉ፣ ብሔርን ከብሔር እና ሃይማኖትን ከሃይማኖት የሚያጋጩ የሕዝብ ለህዝብ ግጭቶች በከፍተኛ ሁኔታ መቀነሳቸውን ገልጸዋል።
👉🏽አሁን የሚታዩት ግጭቶች የሕዝብ ለሕዝብ ሳይሆኑ፣ ኢትዮጵያን ማፍረስ በሚፈልጉ ኃይሎች የሚደገፉ "ሽፍቶች እና ባንዳዎች" የሚፈጥሩት መሆኑን ገልጸዋል። የፀጥታ ተቋማት (Law Enforcement Agencies) በሰው ኃይልም ሆነ በቴክኖሎጂ አቅማቸውን እያሳደጉ መሆኑን አረጋግጠዋል።
👉🏽በኦሮሚያም ሆነ በአማራ ክልል ያሉ የታጠቁ ኃይሎች ግጭት ወደ ድል ስለማያደርስ፣ ውይይት እና ድርድርን መርጠው ወደ ሰላማዊ መንገድ እንዲመለሱና በጋራ ሀገር እንዲገነቡ የሰላም ጥሪ አቅርበዋል።
#ethiopia #parliament #pmabiyahmed #politics #ebc
**********************
👉🏽ላለፉት አምስት ዓመታት በምክር ቤቱ ውስጥ የሕዝብን እና የፓርቲያቸውን ድምጽ ሲያሰሙ ለነበሩ የተፎካካሪ ፓርቲ አባላት (እንደ ኢዜማ፣ አብን እና ሌሎችም) እንዲሁም ለብልጽግና አባላት ከፍተኛ ምስጋና አቅርበዋል።
👉🏽በዘንድሮው ምርጫ ምክንያት ወደ ምክር ቤት ለማይመለሱ የተፎካካሪ ፓርቲ አባላት፣ የመንግሥት ፍላጎት በጋራ መሥራት መሆኑን በመግለጽ፤ ከምክር ቤት ውጭም ቢሆን ሀገርን ለማልማት ከመንግሥት ጋር አብረው እንዲሠሩ ጥሪ አቅርበዋል።
👉🏽የዘንድሮው ምርጫ ከተለመደው የፖለቲካ ፉክክር ባለፈ፣ ራሱ ምርጫው እንዳይካሄድ በ"ባንዳዎች" እና ፀረ-ምርጫ ኃይሎች ከፍተኛ ጫና እና ማሸማቀቅ እንደነበረበት አንስተዋል።
👉🏽ሕዝቡ ማስፈራሪያዎችን ወደጎን በመተው ሌሊት ወጥቶ በመሰለፍ ድምፁን መስጠቱን፤ በዚህም ፅንፈኝነትን፣ ባንዳነትን እና ዘረኝነትን እንደማይፈልግ በአንድ ድምፅ ማሳየቱን ገልጸዋል።
👉🏽ሕዝቡ ለመንግሥት ጅምር ሥራዎች ዕውቅና በመስጠት ድምፁን ቢሰጥም፣ ይህ ድምጽ "ባዶ ቼክ" መሆኑን አሳስበዋል።
👉🏽ሕዝቡ ሥርአታዊ ሌብነት (ሙስና) እንዲጠፋ እና አገልግሎት እንዲሻሻል አደራ መስጠቱን፤ ይህን አደራ መንግሥት በአግባቡ ካልተወጣ፣ ጥይት ሳይፈራ የመረጠው ሕዝብ በተመሳሳይ ድፍረት የተቃውሞ እርምጃ ሊወስድ እንደሚችል አስጠንቅቀዋል።
👉🏽ብልጽግና ፓርቲ ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ ሲል፣ 15 በመቶ የሚሆነውን የምክር ቤት ወንበር ተፎካካሪ ፓርቲዎች ብቻቸውን እንዲወዳደሩበት ማድረጉን እና ይህም በርካታ ፓርቲዎች ፓርላማ እንዲገቡ ዕድል መፍጠሩን አብራርተዋል።
👉🏽በሀገራዊ ምክክሩ ላይ ብልጽግና ፓርቲ ይዞት ከሚቀርባቸው አጀንዳዎች አንዱ፣ በሥልጣን ላይ ያለ መንግሥት (መሪ) ከሁለት የምርጫ ዘመን በላይ መቆየት የለበትም የሚል የሕገ-መንግስት ማሻሻያ ሀሳብ መሆኑን አስታውቀዋል።
👉🏽ጠቅላይ ሚኒስትሩ ራሳቸው ከ225 በላይ፣ ፓርቲው ደግሞ ከ4 ሺህ በላይ የሕዝብ መድረኮችን ማካሄዱን፤ እንዲሁም የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽኑ የሕዝብ ውይይቶችን በስፋት እያደረገ መሆኑን አንስተዋል።
👉🏽ታፍነው የቆዩ ብሶቶች በነጻነት እንዲወጡ በመደረጉ፣ ብሔርን ከብሔር እና ሃይማኖትን ከሃይማኖት የሚያጋጩ የሕዝብ ለህዝብ ግጭቶች በከፍተኛ ሁኔታ መቀነሳቸውን ገልጸዋል።
👉🏽አሁን የሚታዩት ግጭቶች የሕዝብ ለሕዝብ ሳይሆኑ፣ ኢትዮጵያን ማፍረስ በሚፈልጉ ኃይሎች የሚደገፉ "ሽፍቶች እና ባንዳዎች" የሚፈጥሩት መሆኑን ገልጸዋል። የፀጥታ ተቋማት (Law Enforcement Agencies) በሰው ኃይልም ሆነ በቴክኖሎጂ አቅማቸውን እያሳደጉ መሆኑን አረጋግጠዋል።
👉🏽በኦሮሚያም ሆነ በአማራ ክልል ያሉ የታጠቁ ኃይሎች ግጭት ወደ ድል ስለማያደርስ፣ ውይይት እና ድርድርን መርጠው ወደ ሰላማዊ መንገድ እንዲመለሱና በጋራ ሀገር እንዲገነቡ የሰላም ጥሪ አቅርበዋል።
#ethiopia #parliament #pmabiyahmed #politics #ebc
1 month ago
Sponsored by
Surafel
1 month ago
u1260u121du122du132bu12cd u12ebu120du1320u1260u1243u127du1201u1275 u123du1295u1348u1275u1293 u12f5u120d u12ebu1308u129bu127du1201u1275 u12e8u1275 u1290u12cd? u12a8u12a2u12dcu121b u1218u122a u12a2u12eeu1265 u1218u1233u134du1295u1275 u130bu122d u12e8u1270u12f0u1228u1308 u1246u12edu1273 #u134bu1293u121au12f2u12ebu12aeu122du1356u122cu123du1295 #fanamediacorporation ","delight_ranges":[],"image_ranges":[],"inline_style_ranges":[],"aggregated_ranges":[],"ranges":[{"entity":{"__typename":"Hashtag","__isEntity":"Hashtag","url":"https://www.facebook.com/h...
በምርጫው ያልጠበቃችሁት ሽንፈትና ድል ያገኛችሁት የት ነው? ከኢዜማ መሪ ኢዮብ መሳፍንት ጋር የተደረገ ቆይታ #ፋናሚዲያኮርፖሬሽን #fanamediacorporation
1 month ago
በጠቅላላ ምርጫው በርካታ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች የምክር ቤት ወንበር ማሸነፋቸው የዴሞክራሲ ምህዳሩን መስፋት ያረጋገጠ ነው፡- የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች
*******************
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በስኬት የተካሄደውን የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ውጤት ይፋ ማድረጉን ተከትሎ፣ በርካታ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች የምክር ቤት ወንበሮችን ማሸነፋቸው በኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ምህዳሩ እየሰፋ መመጣቱን በተግባር ያሳየ መሆኑን የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች ገለጹ።
ይህ ስኬት በክልል እና በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የተሻለ የሀሳብ ብዝኃነት እንዲኖርና ጠንካራ የመንግሥት ተቋማትን የመገንባት ሂደትን ለማሳካት ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳለው ተጠቁሟል።
በተገለጸው የምርጫ ውጤት መሠረት ብልፅግና ፓርቲ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 438 መቀመጫዎችን ሲያገኝ፤ ኢዜማ 13፣ አብን 6፣ ነእፓ 3፣ መድረክ 3፣ አዴኃን 3፣ ትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት 2 ወንበሮችን ያሸነፉ ሲሆን ሌሉች 10 ተፎካካሪ ፓርቲዎች ደግሞ እያንዳንዳቸው አንድ የምክር ቤት ወንበር አግኝተዋል።
ለክልል ምክር ቤት በተደረገው ውድድርም ኢዜማ 73፣ ነእፓ 35፣ ሰላም ለኢትዮጵያ ጥምረት 34፣ ኦብነግ 20፣ ጉህዴን 14፣ መድረክ 11፣ ትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት 6፣ ሕዳሴ ፓርቲ 5 እና ቤህነን 5 ወንበሮችን ማሸነፍ ችለዋል።
የነጻነትና እኩልነት ፓርቲ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ወይዘሮ ነቢሃ መሀመድ ምርጫው የሕዝብ ድምፅ መንግሥት ለመመስረት ብቸኛው መንገድ መሆኑንና መንግሥት የሚመሰረተው በኃይል ሳይሆን በሐሳብ ብቻ መሆኑን ያስተማረ ነው ማለታቸውን ኢዜአ ዘግቧል።
አያይዘውም ፓርቲያቸው በሀገራዊ ጥቅም፣ በሉዓላዊነት፣ በወጣቶች የሥራ ዕድል ፈጠራና በምግብ ዋስትና ዙሪያ ከብልጽግና ፓርቲ ጋር በትብብር ለመሥራት ዝግጁ መሆኑን አረጋግጠዋል።
በሌላ በኩል የወሎ ሕዝቦች ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ ፕሬዝዳንት አቶ ነጻነት ጣሰው ከተፎካካሪ ፓርቲዎች ጋር እስከ ታችኛው መዋቅር ተቀራርቦ መሥራት ሀገር ለማሻገር ቁልፍ ሚና እንዳለው በመጥቀስ፣ ለሀገረ መንግሥት ግንባታና ለሀገራዊ ምክክሩ መሳካት ፓርቲያቸው የፖሊሲ ምክረ ሐሳቦችን በጥናት ለይቶ በማቅረብ ኃላፊነቱን እንደሚወጣ አስታውቀዋል።
#ethiopiaelections #democracy #politicalpluralism #nationalunity #ethiopianbroadcastingcorporation
*******************
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በስኬት የተካሄደውን የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ውጤት ይፋ ማድረጉን ተከትሎ፣ በርካታ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች የምክር ቤት ወንበሮችን ማሸነፋቸው በኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ምህዳሩ እየሰፋ መመጣቱን በተግባር ያሳየ መሆኑን የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች ገለጹ።
ይህ ስኬት በክልል እና በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የተሻለ የሀሳብ ብዝኃነት እንዲኖርና ጠንካራ የመንግሥት ተቋማትን የመገንባት ሂደትን ለማሳካት ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳለው ተጠቁሟል።
በተገለጸው የምርጫ ውጤት መሠረት ብልፅግና ፓርቲ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 438 መቀመጫዎችን ሲያገኝ፤ ኢዜማ 13፣ አብን 6፣ ነእፓ 3፣ መድረክ 3፣ አዴኃን 3፣ ትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት 2 ወንበሮችን ያሸነፉ ሲሆን ሌሉች 10 ተፎካካሪ ፓርቲዎች ደግሞ እያንዳንዳቸው አንድ የምክር ቤት ወንበር አግኝተዋል።
ለክልል ምክር ቤት በተደረገው ውድድርም ኢዜማ 73፣ ነእፓ 35፣ ሰላም ለኢትዮጵያ ጥምረት 34፣ ኦብነግ 20፣ ጉህዴን 14፣ መድረክ 11፣ ትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት 6፣ ሕዳሴ ፓርቲ 5 እና ቤህነን 5 ወንበሮችን ማሸነፍ ችለዋል።
የነጻነትና እኩልነት ፓርቲ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ወይዘሮ ነቢሃ መሀመድ ምርጫው የሕዝብ ድምፅ መንግሥት ለመመስረት ብቸኛው መንገድ መሆኑንና መንግሥት የሚመሰረተው በኃይል ሳይሆን በሐሳብ ብቻ መሆኑን ያስተማረ ነው ማለታቸውን ኢዜአ ዘግቧል።
አያይዘውም ፓርቲያቸው በሀገራዊ ጥቅም፣ በሉዓላዊነት፣ በወጣቶች የሥራ ዕድል ፈጠራና በምግብ ዋስትና ዙሪያ ከብልጽግና ፓርቲ ጋር በትብብር ለመሥራት ዝግጁ መሆኑን አረጋግጠዋል።
በሌላ በኩል የወሎ ሕዝቦች ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ ፕሬዝዳንት አቶ ነጻነት ጣሰው ከተፎካካሪ ፓርቲዎች ጋር እስከ ታችኛው መዋቅር ተቀራርቦ መሥራት ሀገር ለማሻገር ቁልፍ ሚና እንዳለው በመጥቀስ፣ ለሀገረ መንግሥት ግንባታና ለሀገራዊ ምክክሩ መሳካት ፓርቲያቸው የፖሊሲ ምክረ ሐሳቦችን በጥናት ለይቶ በማቅረብ ኃላፊነቱን እንደሚወጣ አስታውቀዋል።
#ethiopiaelections #democracy #politicalpluralism #nationalunity #ethiopianbroadcastingcorporation
1 month ago
የሥልጣን መያዣው መንገድ በምርጫ ብቻ መሆን እንዳለበት ሕዝቡ በተግባር አሳይቷል፡- የኢዜማ መሪ አቶ እዮብ መሳፍንት
**********************
የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ (ኢዜማ) መሪ አቶ እዮብ መሳፍንት ከኢቲቪ ወቅታዊ ጋር ባደረጉት ቆይታ፣ የድህረ ምርጫ ወቅታዊ ሁኔታዎችንና የፓርቲያቸውን የቀጣይ የፖለቲካ አቅጣጫ በተመለከተ ሰፊ ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡
መሪው በምርጫው ወቅት የታየውን ከፍተኛ የሕዝብ ተሳትፎ ያደነቁ ሲሆን፣ ሕዝቡ በተለያዩ ተግዳሮቶች ሳይበግረው ረጅም ሰዓት ተሰልፎ መምረጡ ከሰላማዊ አማራጭ ውጪ በጠመንጃ ሥልጣን የመያዝ አባዜ ከኢትዮጵያ የፖለቲካ ባህል ውስጥ ሙሉ በሙሉ መወገድ እንዳለበት ያሳየበት ግልጽ መልዕክት ነው ብለዋል፡፡
ኢዜማ ወደ ምርጫው የገባው የኢትዮጵያን ተጨባጭ የፖለቲካ ምኅዳር በጥልቀት ገምግሞ መሆኑን የገለጹት አቶ እዮብ፣ ፓርቲው አስቀድሞ ካስቀመጠው ግብ አንጻር የአሁኑ ተሳትፎው ከሞላ ጎደል ስኬታማ እንደነበርና ምርጫ ሲደርስ ብቻ የሚደናገጥ ሳይሆን ራሱን ወዲያውኑ ለቀጣዩ ምርጫ ማዘጋጀት መጀመሩን አስታውቀዋል፡፡
ኢዜማ በክልልና በፌደራል ምክር ቤቶች በድምሩ 86 ወንበሮች ማግኘቱን የጠቀሱት መሪው፣ እነዚህን ወንበሮች በመጠቀም አማራጭ ፖሊሲዎችን ወደፊት ለመግፋትና መንግሥትን ለመጠየቅ በቁርጠኝነት እንደሚሰሩበት አረጋግጠዋል፡፡
አያይዘውም አሁን ለተመረጠው መንግሥት የተሰጠው ኃላፊነት ከተጠያቂነት ጋር የተሰጠ ሕዝባዊ አደራ እንጂ እንደፈለጉ የሚፈነጩበት ሥልጣን አለመሆኑን አሳስበዋል፡፡
በኢትዮጵያ ያለው የምርጫ ሥርዓት ተቀይሮ የአንድም ዜጋ ድምፅ እንዳይባክን የሚያደርግ “የተመጣጣኝ ውክልና ሥርዓት” ሊተገበር እንደሚገባ ፓርቲያቸው በፅኑ እንደሚያምንና ኢትዮጵያ ውስጥ ከፖለቲካና ከዘውግ ወገንተኝነት የጸዱ፣ በእውቀት ላይ የተመሰረቱ ገለልተኛ ተቋማትን (Institutions) ለመገንባት የገዥው ፓርቲ ቀዳሚ ኃላፊነት ቢሆንም የሁላችንም የጋራ ርብርብ ያስፈልገናል ብለዋል፡፡
የባሕር በር ጉዳይን በተመለከተ ማብራሪያ የሰጡት አቶ እዮብ መሳፍንት፣ የባሕር በር ጥያቄ የቅንጦት ሳይሆን ከ120 ሚሊዮን በላይ ሕዝብ ላላት ሀገር የልማት፣ የዕድገትና የደኅንነት ዋስትና መሆኑን ገልጸዋል።
ይህንን ብሔራዊ ጥቅም ከፊት ሆኖ ከሚያራምድ ከማንኛውም አካልና ከመንግሥት ጋር በትብብር ለመሥራት ፓርቲያቸው ዝግጁ መሆኑን በድፍረት ተናግረዋል፡፡
በመሐመድ ፊጣሞ
#ethiopianelection #ezema #peacefulpolitics #nationalinterest #ethiopianbroadcastingcorporation
**********************
የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ (ኢዜማ) መሪ አቶ እዮብ መሳፍንት ከኢቲቪ ወቅታዊ ጋር ባደረጉት ቆይታ፣ የድህረ ምርጫ ወቅታዊ ሁኔታዎችንና የፓርቲያቸውን የቀጣይ የፖለቲካ አቅጣጫ በተመለከተ ሰፊ ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡
መሪው በምርጫው ወቅት የታየውን ከፍተኛ የሕዝብ ተሳትፎ ያደነቁ ሲሆን፣ ሕዝቡ በተለያዩ ተግዳሮቶች ሳይበግረው ረጅም ሰዓት ተሰልፎ መምረጡ ከሰላማዊ አማራጭ ውጪ በጠመንጃ ሥልጣን የመያዝ አባዜ ከኢትዮጵያ የፖለቲካ ባህል ውስጥ ሙሉ በሙሉ መወገድ እንዳለበት ያሳየበት ግልጽ መልዕክት ነው ብለዋል፡፡
ኢዜማ ወደ ምርጫው የገባው የኢትዮጵያን ተጨባጭ የፖለቲካ ምኅዳር በጥልቀት ገምግሞ መሆኑን የገለጹት አቶ እዮብ፣ ፓርቲው አስቀድሞ ካስቀመጠው ግብ አንጻር የአሁኑ ተሳትፎው ከሞላ ጎደል ስኬታማ እንደነበርና ምርጫ ሲደርስ ብቻ የሚደናገጥ ሳይሆን ራሱን ወዲያውኑ ለቀጣዩ ምርጫ ማዘጋጀት መጀመሩን አስታውቀዋል፡፡
ኢዜማ በክልልና በፌደራል ምክር ቤቶች በድምሩ 86 ወንበሮች ማግኘቱን የጠቀሱት መሪው፣ እነዚህን ወንበሮች በመጠቀም አማራጭ ፖሊሲዎችን ወደፊት ለመግፋትና መንግሥትን ለመጠየቅ በቁርጠኝነት እንደሚሰሩበት አረጋግጠዋል፡፡
አያይዘውም አሁን ለተመረጠው መንግሥት የተሰጠው ኃላፊነት ከተጠያቂነት ጋር የተሰጠ ሕዝባዊ አደራ እንጂ እንደፈለጉ የሚፈነጩበት ሥልጣን አለመሆኑን አሳስበዋል፡፡
በኢትዮጵያ ያለው የምርጫ ሥርዓት ተቀይሮ የአንድም ዜጋ ድምፅ እንዳይባክን የሚያደርግ “የተመጣጣኝ ውክልና ሥርዓት” ሊተገበር እንደሚገባ ፓርቲያቸው በፅኑ እንደሚያምንና ኢትዮጵያ ውስጥ ከፖለቲካና ከዘውግ ወገንተኝነት የጸዱ፣ በእውቀት ላይ የተመሰረቱ ገለልተኛ ተቋማትን (Institutions) ለመገንባት የገዥው ፓርቲ ቀዳሚ ኃላፊነት ቢሆንም የሁላችንም የጋራ ርብርብ ያስፈልገናል ብለዋል፡፡
የባሕር በር ጉዳይን በተመለከተ ማብራሪያ የሰጡት አቶ እዮብ መሳፍንት፣ የባሕር በር ጥያቄ የቅንጦት ሳይሆን ከ120 ሚሊዮን በላይ ሕዝብ ላላት ሀገር የልማት፣ የዕድገትና የደኅንነት ዋስትና መሆኑን ገልጸዋል።
ይህንን ብሔራዊ ጥቅም ከፊት ሆኖ ከሚያራምድ ከማንኛውም አካልና ከመንግሥት ጋር በትብብር ለመሥራት ፓርቲያቸው ዝግጁ መሆኑን በድፍረት ተናግረዋል፡፡
በመሐመድ ፊጣሞ
#ethiopianelection #ezema #peacefulpolitics #nationalinterest #ethiopianbroadcastingcorporation
Sponsored by
Surafel
1 month ago
1 month ago
ከወንበር በላይ ሀገር !
የምርጫ ቦርድ የዘንድሮውን ሀገራዊ ምርጫ ውጤት ይፋ ውጤት የሀገሪቱን የፖለቲካ ካርታ ግልጽ አድርጎታል። ገዥው ብልጽግና ፓርቲ አብላጫውን ወንበር ወስዷል፤ ሀገራችንም ወደ ሌላ አዲስ የፖለቲካ ምዕራፍ ተሻግራለች።
ኢዜማ የለፋውን እና የደከመበትን ያህል ባይሆንም 86 ወንበሮችን አሸንፏል (13ቱ በፌደራል ፓርላማ፣ 73ቱ በክልል ምክር ቤቶች) በዚህ ውጤቱ ኢዜማ በፓርላማው ውስጥ ዋነኛው ተፎካካሪና አማራጭ ድምፅ ሆኖ ወጥቷል። ለመሆኑ ይህ ውጤት የለፋንለትና የተመኘነው ያህል ነው? ፈጽሞ አይደለም። ታዲያ በቀላሉ የምናጣጥለው እና ፋይዳቢስ የሚባልስ ነው? በፍጹም!
ፖለቲካ እንደ ሎተሪ ዕጣ በአንድ ጀምበር ሁሉንም እድል ጠራርጎ የሚወሰድበት ወይንም በተቃራኒው ሁሉንም ተበልቶ በባዶ እጅ እየቆዘሙ አንገት ደፍቶ ወደቤት የሚኬድበት የዕድል ጨዋታ አይደለም። ለኢዜማ 86 ወንበሮች በማሸነፍ፣ ጠንካራ መዋቅርን ለመሥራት እና ቀጣዩ ምርጫ እስኪደርስ መላውን አባላት በንቃት የሚያሳትፍ በርካታ የቤት ሥራ ይዞ መውጣትም በፖለቲካ ዐይን ተጨማሪ የዴሞክራሲ እርምጃ ነው።
ከእኛ ጋር ተፎካካሪ የነበሩ፤ የሕዝብ አመኔታ እና ድምጽ ሲያጡ እና እንዳለሙት ውጤት ሳይቀናቸው ሲቀር፣ የሌላውን ድካምና ውጤት ለማጣጣል እና ስም ለመለጠፍ የሚሮጡትን "አንዳንድ የተቃውሞ ነዋሪዎች" ስናይ... "ያጣ ለማኝ ተሳድቦ ይሄዳል" ከሚለው ነባር የሀገራችን ብሂል የተሻለ ምን ማስተማሪያ ሊገኝላቸው ይችላል?
ሌሎች ደግሞ አሉ። ዓላማቸው ከዓላማችን፤ መንገዳቸውም ከመንገዳችን ስላልገጠመ ብቻ ማኅበራዊ ሚዲያ ላይ ተጥደው ሲረግሙን ውለው ሲረግሙን በማደራቸው ፖለቲካ የተነተኑ የሚመስላቸው የቁራ ጯሂዎች! የተለመደው ቁርጥ ያለ መልሳቸን “ያዋጣል በምትሉት መንገድ ሂዱ! የእኛን መንገድ ለእኛ ተዉልን” የሚል ይሆናል። ዳር ቆመው ሰባራ ሳንቲም ሳያዋጡ ተዓምር ለሚናፍቁ የሰነፍ ቅምጥሎችና ‘የሶሻል ሚዲያ አርበኞች’ መልካም የምኞት ጊዜ ይሁንላቸው ከማለት ውጪስ ምን ይባላል?
እኛ ኢዜማውያን ግን ዲሞክራሲ የሚገነባው እጅጌን ሰብስቦ እና ቆፍጠን ብሎ መሬት ላይ ሥራ በመሥራት መሆኑን ስለምናምን ከባለፈው የምርጫ ተሳትፎአችን በብዙ እጥፍ የጨመረውን ውጤት በጸጋ ተቀብለን እና የሕዝብ ድምጽ አክብረን በጨዋነት እና በስለጠነ ዘመናዊ ፖለቲካ ተሳትፎ ወደፊት እንራመዳለን። በውድድር ውስጥ ማሸነፍን ብቻ ሳይሆን፣ ተሸንፎም ትልቁን ሀገራዊ ስዕል ማየት መቻል የፖለቲካ ብስለት መለኪያ ነውና።
አሁን የምርጫው አጀንዳ ከሞላ ጎደል ተጠናቅቋል፤ አሸናፊዎች ወደየምክር ቤቶቻቸው፤ የተቀረነውም ወደየ እለታዊ ተግባራችን እንመለሳለን። ሀገርን ማገልገል በምክር ቤቶች ተሳትፎ ብቻ አይወሰንም። የሀገር ግንባታ በምርምር ማዕከላት፣ በዩኒቨርሲቲዎች፣ በሙያ ማኅበራት፤ በሲቪክ መድረኮች፣ በልዩ ልዩ የማኅበረሰብ ከገልግሎቶች ውስጥ ይቀጥላል።
… እንዲያውም ሁሉም ሰው በድንገት የሕገ-መንግስት ተንታኝ፣ የጂኦፖለቲካው ነብይ፣ የፌደራሊዝም ሐዋርያ በሚሆንበት በዚያ ድራማዊ የቡና ጠረጴዛ ውይይት ውስጥ ጭምር ሕይወት እንደወትሮው ይቀጥላል።
እስካሁን የተጓዝንበትን ለሀገር እና ለወገን የሚጠቅም የፖለቲካ ተሳትፎን በኩራት እያከበርን፤ አሁን ደግሞ የፓርቲ ማሊያችንን አውልቀን፣ የሙያ ጃኬታችንን ለብሰን ወደ ዋናው ሥራችን ብንመለስ ምን ይለናል? የሽሚዞቻችን እጅጌ ስብስበን "ዳዬ ወደሥራ!" ብለናል።
እግረመንገድም ከአድካሚው እና እንደ ልቅሶ ቤት አግዳሚ ወንበር ከሊቅ እስከ ደቂቅ አኩል ተኮልኩሎ ከፊሉ ሲራገም ከፊሉ ሲመርቅ ከሚውልበት የማኅበራዊ ሚዲያ መድረክም እስከውዲያኛውም ባይሆንም እረፍት መውጣት ተገቢ አይደለም ትላላቸሁ?
መልክም ጊዜ !
(አርኪቴክት ዮሐንስ መኮንን የኢዜማ ከፍተኛ አመራር)
#ኢትዮጵያ #ኢዜማ #ሀገርግንባታ #ምርጫ2018 #ዲሞክራሲ
የምርጫ ቦርድ የዘንድሮውን ሀገራዊ ምርጫ ውጤት ይፋ ውጤት የሀገሪቱን የፖለቲካ ካርታ ግልጽ አድርጎታል። ገዥው ብልጽግና ፓርቲ አብላጫውን ወንበር ወስዷል፤ ሀገራችንም ወደ ሌላ አዲስ የፖለቲካ ምዕራፍ ተሻግራለች።
ኢዜማ የለፋውን እና የደከመበትን ያህል ባይሆንም 86 ወንበሮችን አሸንፏል (13ቱ በፌደራል ፓርላማ፣ 73ቱ በክልል ምክር ቤቶች) በዚህ ውጤቱ ኢዜማ በፓርላማው ውስጥ ዋነኛው ተፎካካሪና አማራጭ ድምፅ ሆኖ ወጥቷል። ለመሆኑ ይህ ውጤት የለፋንለትና የተመኘነው ያህል ነው? ፈጽሞ አይደለም። ታዲያ በቀላሉ የምናጣጥለው እና ፋይዳቢስ የሚባልስ ነው? በፍጹም!
ፖለቲካ እንደ ሎተሪ ዕጣ በአንድ ጀምበር ሁሉንም እድል ጠራርጎ የሚወሰድበት ወይንም በተቃራኒው ሁሉንም ተበልቶ በባዶ እጅ እየቆዘሙ አንገት ደፍቶ ወደቤት የሚኬድበት የዕድል ጨዋታ አይደለም። ለኢዜማ 86 ወንበሮች በማሸነፍ፣ ጠንካራ መዋቅርን ለመሥራት እና ቀጣዩ ምርጫ እስኪደርስ መላውን አባላት በንቃት የሚያሳትፍ በርካታ የቤት ሥራ ይዞ መውጣትም በፖለቲካ ዐይን ተጨማሪ የዴሞክራሲ እርምጃ ነው።
ከእኛ ጋር ተፎካካሪ የነበሩ፤ የሕዝብ አመኔታ እና ድምጽ ሲያጡ እና እንዳለሙት ውጤት ሳይቀናቸው ሲቀር፣ የሌላውን ድካምና ውጤት ለማጣጣል እና ስም ለመለጠፍ የሚሮጡትን "አንዳንድ የተቃውሞ ነዋሪዎች" ስናይ... "ያጣ ለማኝ ተሳድቦ ይሄዳል" ከሚለው ነባር የሀገራችን ብሂል የተሻለ ምን ማስተማሪያ ሊገኝላቸው ይችላል?
ሌሎች ደግሞ አሉ። ዓላማቸው ከዓላማችን፤ መንገዳቸውም ከመንገዳችን ስላልገጠመ ብቻ ማኅበራዊ ሚዲያ ላይ ተጥደው ሲረግሙን ውለው ሲረግሙን በማደራቸው ፖለቲካ የተነተኑ የሚመስላቸው የቁራ ጯሂዎች! የተለመደው ቁርጥ ያለ መልሳቸን “ያዋጣል በምትሉት መንገድ ሂዱ! የእኛን መንገድ ለእኛ ተዉልን” የሚል ይሆናል። ዳር ቆመው ሰባራ ሳንቲም ሳያዋጡ ተዓምር ለሚናፍቁ የሰነፍ ቅምጥሎችና ‘የሶሻል ሚዲያ አርበኞች’ መልካም የምኞት ጊዜ ይሁንላቸው ከማለት ውጪስ ምን ይባላል?
እኛ ኢዜማውያን ግን ዲሞክራሲ የሚገነባው እጅጌን ሰብስቦ እና ቆፍጠን ብሎ መሬት ላይ ሥራ በመሥራት መሆኑን ስለምናምን ከባለፈው የምርጫ ተሳትፎአችን በብዙ እጥፍ የጨመረውን ውጤት በጸጋ ተቀብለን እና የሕዝብ ድምጽ አክብረን በጨዋነት እና በስለጠነ ዘመናዊ ፖለቲካ ተሳትፎ ወደፊት እንራመዳለን። በውድድር ውስጥ ማሸነፍን ብቻ ሳይሆን፣ ተሸንፎም ትልቁን ሀገራዊ ስዕል ማየት መቻል የፖለቲካ ብስለት መለኪያ ነውና።
አሁን የምርጫው አጀንዳ ከሞላ ጎደል ተጠናቅቋል፤ አሸናፊዎች ወደየምክር ቤቶቻቸው፤ የተቀረነውም ወደየ እለታዊ ተግባራችን እንመለሳለን። ሀገርን ማገልገል በምክር ቤቶች ተሳትፎ ብቻ አይወሰንም። የሀገር ግንባታ በምርምር ማዕከላት፣ በዩኒቨርሲቲዎች፣ በሙያ ማኅበራት፤ በሲቪክ መድረኮች፣ በልዩ ልዩ የማኅበረሰብ ከገልግሎቶች ውስጥ ይቀጥላል።
… እንዲያውም ሁሉም ሰው በድንገት የሕገ-መንግስት ተንታኝ፣ የጂኦፖለቲካው ነብይ፣ የፌደራሊዝም ሐዋርያ በሚሆንበት በዚያ ድራማዊ የቡና ጠረጴዛ ውይይት ውስጥ ጭምር ሕይወት እንደወትሮው ይቀጥላል።
እስካሁን የተጓዝንበትን ለሀገር እና ለወገን የሚጠቅም የፖለቲካ ተሳትፎን በኩራት እያከበርን፤ አሁን ደግሞ የፓርቲ ማሊያችንን አውልቀን፣ የሙያ ጃኬታችንን ለብሰን ወደ ዋናው ሥራችን ብንመለስ ምን ይለናል? የሽሚዞቻችን እጅጌ ስብስበን "ዳዬ ወደሥራ!" ብለናል።
እግረመንገድም ከአድካሚው እና እንደ ልቅሶ ቤት አግዳሚ ወንበር ከሊቅ እስከ ደቂቅ አኩል ተኮልኩሎ ከፊሉ ሲራገም ከፊሉ ሲመርቅ ከሚውልበት የማኅበራዊ ሚዲያ መድረክም እስከውዲያኛውም ባይሆንም እረፍት መውጣት ተገቢ አይደለም ትላላቸሁ?
መልክም ጊዜ !
(አርኪቴክት ዮሐንስ መኮንን የኢዜማ ከፍተኛ አመራር)
#ኢትዮጵያ #ኢዜማ #ሀገርግንባታ #ምርጫ2018 #ዲሞክራሲ
2 months ago
ኢዜማ ለምርጫ አሸናፊው ብልፅግና ፓርቲ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላለፈ
የሀገር አቀፉ ምርጫ 2018 ውጤት ይፋ መሆኑን ተከትሎ ከኢዜማ የተሠጠ መግለጫ!!
ሀገር አቀፉ ምርጫ 2018 መጠናቀቁን በትላንትናው ዕለት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ይፋዊ የምርጫ ውጤት በማሣወቅ አረጋግጧል፤ ምርጫው ከነእንከኖቹም ቢሆን በሰላም በመጠናቀቁ ፓርቲያችን እንኳን ደስ አለን ለማለት ይወዳል።
በተጨማሪም ፓርቲያችን ለውድድር በቀረበባቸው ቦታዎች 13 የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እና 73 የክልል እና የከተማ ምክር ቤት ወንበሮችን በድምሩ 86 መቀመጫዎችን በማግኘት በሀገር አቀፍ ደረጃ ቀዳሚው ተፎካካሪ ፓርቲ ሆኖ አጠናቋል። ይህንን ተጨባጭ ስኬት ላስመዘገቡ የፓርቲያችን ዕጩዎች፣ አባላት፣ ደጋፊዎች እና በሂደቱ በቅንነት ለተሳተፉ አካላት ሁሉ እንኳን ደስ አለን እንኳን ደስ አላችሁ ለማለት ይወዳል።
ፓርቲያችን ከቀጣዩ ምርጫ በፊት ባሉት ዓመታት ጠንካራ ጎኖቹን በማስቀጠል እንዲሁም የነበሩበትን ክፍተቶች በስትራቴጂ እና ሌሎች አስፈላጊ ተግባራት በመሙላት ተጨባጭ የተፎካካሪ ፓርቲነት ሚናውን ጊዜ ሳያባክን የሚጀምረው ዛሬ መሆኑን እየገለፅን፤ በነዚህ ዓመታት ከዚህ ቀደም ስናደርገው እንደነበረ ሁሉ ብሔራዊ ጥቅሞችን በሚያሣኩ ጉዳዮች ከሁሉም ኢትዮጵያዊ ኃይል ጋር በመተባበር የምንንቀሳቀስበት መፎካከሪያ አጀንዳዎች ላይ ማኅበረሰባችንን በሚመጥን ጨዋነት ልዩነቶቻችንን እና ትችቶቻችንን እያቀረብን የጀመርነውን ጤናማና ዘመናዊ የፖለቲካ ባሕል የማዋለድ ተግባራችንን በተጠናከረ መልኩ የምንቀጥልበት እንዲሁም ለተጨማሪ ስኬት የምንንደረደርበት እንደሚሆን ቃል እንገባለን።
በመጨረሻም ገዢ ሆኖ እንዲቀጥል ለተመረጠው ብልጽግና ፓርቲ እንዲሁም በውድድሩ ተሳትፋችሁ የሕዝብ ውክልናን ላሳካችሁ ተፎካካሪዎች እንኳን ደስ አላችሁ ለማለት እንወዳለን።
አሸናፊው ፓርቲ ከዛሬ ጀምሮ ዴሞክራሲያዊ ተቋማትን ለመገንባትና ፍትሐዊ የፖለቲካ ምህዳርን ለሁሉም እኩል ተደራሽ ለማድረግ በቁርጠኝነት እንዲሠራ፤ ለሀገር እድገትና ለውጥ ጠቃሚ ሀሳቦች ከማንኛውም ወገን ሊገኙ እንደሚችሉ በመረዳት አማራጭ ሃሳቦችን እንዲሰማ፤ እንዲሁም ትችቶችን በሆደ ሰፊነት እያስተናገደ ሀገራችን የሚያስፈልጋትን ዴሞክራሲ በጋራ እንድንገነባ ጥሪ እናቀርባለን።
ኢዜማ
የሀገር አቀፉ ምርጫ 2018 ውጤት ይፋ መሆኑን ተከትሎ ከኢዜማ የተሠጠ መግለጫ!!
ሀገር አቀፉ ምርጫ 2018 መጠናቀቁን በትላንትናው ዕለት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ይፋዊ የምርጫ ውጤት በማሣወቅ አረጋግጧል፤ ምርጫው ከነእንከኖቹም ቢሆን በሰላም በመጠናቀቁ ፓርቲያችን እንኳን ደስ አለን ለማለት ይወዳል።
በተጨማሪም ፓርቲያችን ለውድድር በቀረበባቸው ቦታዎች 13 የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እና 73 የክልል እና የከተማ ምክር ቤት ወንበሮችን በድምሩ 86 መቀመጫዎችን በማግኘት በሀገር አቀፍ ደረጃ ቀዳሚው ተፎካካሪ ፓርቲ ሆኖ አጠናቋል። ይህንን ተጨባጭ ስኬት ላስመዘገቡ የፓርቲያችን ዕጩዎች፣ አባላት፣ ደጋፊዎች እና በሂደቱ በቅንነት ለተሳተፉ አካላት ሁሉ እንኳን ደስ አለን እንኳን ደስ አላችሁ ለማለት ይወዳል።
ፓርቲያችን ከቀጣዩ ምርጫ በፊት ባሉት ዓመታት ጠንካራ ጎኖቹን በማስቀጠል እንዲሁም የነበሩበትን ክፍተቶች በስትራቴጂ እና ሌሎች አስፈላጊ ተግባራት በመሙላት ተጨባጭ የተፎካካሪ ፓርቲነት ሚናውን ጊዜ ሳያባክን የሚጀምረው ዛሬ መሆኑን እየገለፅን፤ በነዚህ ዓመታት ከዚህ ቀደም ስናደርገው እንደነበረ ሁሉ ብሔራዊ ጥቅሞችን በሚያሣኩ ጉዳዮች ከሁሉም ኢትዮጵያዊ ኃይል ጋር በመተባበር የምንንቀሳቀስበት መፎካከሪያ አጀንዳዎች ላይ ማኅበረሰባችንን በሚመጥን ጨዋነት ልዩነቶቻችንን እና ትችቶቻችንን እያቀረብን የጀመርነውን ጤናማና ዘመናዊ የፖለቲካ ባሕል የማዋለድ ተግባራችንን በተጠናከረ መልኩ የምንቀጥልበት እንዲሁም ለተጨማሪ ስኬት የምንንደረደርበት እንደሚሆን ቃል እንገባለን።
በመጨረሻም ገዢ ሆኖ እንዲቀጥል ለተመረጠው ብልጽግና ፓርቲ እንዲሁም በውድድሩ ተሳትፋችሁ የሕዝብ ውክልናን ላሳካችሁ ተፎካካሪዎች እንኳን ደስ አላችሁ ለማለት እንወዳለን።
አሸናፊው ፓርቲ ከዛሬ ጀምሮ ዴሞክራሲያዊ ተቋማትን ለመገንባትና ፍትሐዊ የፖለቲካ ምህዳርን ለሁሉም እኩል ተደራሽ ለማድረግ በቁርጠኝነት እንዲሠራ፤ ለሀገር እድገትና ለውጥ ጠቃሚ ሀሳቦች ከማንኛውም ወገን ሊገኙ እንደሚችሉ በመረዳት አማራጭ ሃሳቦችን እንዲሰማ፤ እንዲሁም ትችቶችን በሆደ ሰፊነት እያስተናገደ ሀገራችን የሚያስፈልጋትን ዴሞክራሲ በጋራ እንድንገነባ ጥሪ እናቀርባለን።
ኢዜማ
2 months ago
ኢዜማ በ7ኛዉ ዙር ሀገር አቀፍ ምርጫ 86 መቀመጫዎችን በማግኘት ቀዳሚዉ ተፎካካሪ ፓርቲ ሆኖ ማጠናቀቁን ገለፀ
የኢትዮጵያ ዜጎች ለማሕበራዊ ፍትሕ ኢዜማ ሀገር አቀፉ ምርጫዉ ከነእንከኖቹም ቢሆን በሰላም በመጠናቀቁ ደስተኛ ነኝ ሲል መግለጫ ሰጥቷል፡፡
ይህን ተከትሎም ፓርቲዉ ለውድድር በቀረበባቸው ቦታዎች 13 የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እና 73 የክልል እና የከተማ ምክር ቤት ወንበሮችን በድምሩ 86 መቀመጫዎችን በማግኘት በሀገር አቀፍ ደረጃ ቀዳሚው ተፎካካሪ ፓርቲ ሆኖ ማጠናቀቁን አስታዉቋል።
ኢዜማ ከቀጣዩ ምርጫ በፊት ባሉት ዓመታት ጠንካራ ጎኖቹን በማስቀጠል እንዲሁም የነበሩበትን ክፍተቶች በስትራቴጂ እና ሌሎች አስፈላጊ ተግባራት በመሙላት ተጨባጭ የተፎካካሪ ፓርቲነት ሚናውን ጊዜ ሳያባክን የሚጀምረው ተግባር መሆኑን ጠቁሟል፡፡
ፓርዉ አክሎም ገዢ ሆኖ እንዲቀጥል ለተመረጠው ብልጽግና ፓርቲ እና ለውድድሩ ተሳታፊዎች የእንኳን ደስያላችሁ መልዕክቱን አሥተላልፏል፡፡
በተጨማሪም አሸናፊው ፓርቲ ከዛሬ ጀምሮ ዴሞክራሲያዊ ተቋማትን ለመገንባትና ፍትሐዊ የፖለቲካ ምህዳርን ለሁሉም እኩል ተደራሽ ለማድረግ በቁርጠኝነት እንዲሠራ፤ አማራጭ ሃሳቦችን እንዲሰማ፤ እንዲሁም ትችቶችን በሆደ ሰፊነት እያስተናገደ የሀገሪቱን ዴሞክራሲ በጋራ ለመገንባት ቁርጠኛ እንዲሆን ጥሪዉን አቅርቧል፡፡
Seledadotio
Seledadotio
የኢትዮጵያ ዜጎች ለማሕበራዊ ፍትሕ ኢዜማ ሀገር አቀፉ ምርጫዉ ከነእንከኖቹም ቢሆን በሰላም በመጠናቀቁ ደስተኛ ነኝ ሲል መግለጫ ሰጥቷል፡፡
ይህን ተከትሎም ፓርቲዉ ለውድድር በቀረበባቸው ቦታዎች 13 የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እና 73 የክልል እና የከተማ ምክር ቤት ወንበሮችን በድምሩ 86 መቀመጫዎችን በማግኘት በሀገር አቀፍ ደረጃ ቀዳሚው ተፎካካሪ ፓርቲ ሆኖ ማጠናቀቁን አስታዉቋል።
ኢዜማ ከቀጣዩ ምርጫ በፊት ባሉት ዓመታት ጠንካራ ጎኖቹን በማስቀጠል እንዲሁም የነበሩበትን ክፍተቶች በስትራቴጂ እና ሌሎች አስፈላጊ ተግባራት በመሙላት ተጨባጭ የተፎካካሪ ፓርቲነት ሚናውን ጊዜ ሳያባክን የሚጀምረው ተግባር መሆኑን ጠቁሟል፡፡
ፓርዉ አክሎም ገዢ ሆኖ እንዲቀጥል ለተመረጠው ብልጽግና ፓርቲ እና ለውድድሩ ተሳታፊዎች የእንኳን ደስያላችሁ መልዕክቱን አሥተላልፏል፡፡
በተጨማሪም አሸናፊው ፓርቲ ከዛሬ ጀምሮ ዴሞክራሲያዊ ተቋማትን ለመገንባትና ፍትሐዊ የፖለቲካ ምህዳርን ለሁሉም እኩል ተደራሽ ለማድረግ በቁርጠኝነት እንዲሠራ፤ አማራጭ ሃሳቦችን እንዲሰማ፤ እንዲሁም ትችቶችን በሆደ ሰፊነት እያስተናገደ የሀገሪቱን ዴሞክራሲ በጋራ ለመገንባት ቁርጠኛ እንዲሆን ጥሪዉን አቅርቧል፡፡
Seledadotio
Seledadotio
2 months ago
የኢዜማ የምርጫ 2018 86 መቀመጫዎችን ማሸነፉን አስታወቀ
#fastmereja I የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የ2018 ሀገር አቀፍ ምርጫ ይፋዊ ውጤትን ይፋ ማድረጉን ተከትሎ፣ የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) በምርጫው ያገኘውን ውጤት በመግለጽ ለቀጣይ የሥራ አቅጣጫዎች ጥሪ አቅርቧል። ፓርቲው በምርጫው በድምሩ 86 መቀመጫዎችን በማሸነፍ አጠናቋል።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ትላንት ባወጣው ይፋዊ ውጤት መሠረት፣ ኢዜማ በሀገር አቀፍ ደረጃ የተወዳደረባቸውን የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 13 ወንበሮች እንዲሁም 73 የክልልና የከተማ ምክር ቤት ወንበሮችን በማሸነፍ አጠቃላይ 86 መቀመጫዎችን ይዟል።
ፓርቲው በሰጠው መግለጫ፣ ምርጫው በሰላም መጠናቀቁን በመጥቀስ ለዕጩዎቹ፣ ለአባላቱ እና ለደጋፊዎቹ የእንኳን ደስ አላችሁ መልእክት አስተላልፏል። ኢዜማ በውጤቱ በመደሰት ብቻ ሳይወሰን፣ የቀጣዮቹን ዓመታት የሥራ አቅጣጫ በግልጽ አስቀምጧል።
ለብልጽግና ፓርቲ የእንኳን ደስ አላችሁ መልእክት ያስተላለፈው ኢዜማ፤ ገዢው ፓርቲ ዴሞክራሲያዊ ተቋማትን በመገንባት፣ ፍትሐዊ የፖለቲካ ምህዳርን በመፍጠር፣ አማራጭ ሀሳቦችን በመቀበል እና ትችቶችን በሆደ ሰፊነት በማስተናገድ ኃላፊነቱን እንዲወጣ ጥሪ አቅርቧል።
#fastmereja I የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የ2018 ሀገር አቀፍ ምርጫ ይፋዊ ውጤትን ይፋ ማድረጉን ተከትሎ፣ የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) በምርጫው ያገኘውን ውጤት በመግለጽ ለቀጣይ የሥራ አቅጣጫዎች ጥሪ አቅርቧል። ፓርቲው በምርጫው በድምሩ 86 መቀመጫዎችን በማሸነፍ አጠናቋል።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ትላንት ባወጣው ይፋዊ ውጤት መሠረት፣ ኢዜማ በሀገር አቀፍ ደረጃ የተወዳደረባቸውን የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 13 ወንበሮች እንዲሁም 73 የክልልና የከተማ ምክር ቤት ወንበሮችን በማሸነፍ አጠቃላይ 86 መቀመጫዎችን ይዟል።
ፓርቲው በሰጠው መግለጫ፣ ምርጫው በሰላም መጠናቀቁን በመጥቀስ ለዕጩዎቹ፣ ለአባላቱ እና ለደጋፊዎቹ የእንኳን ደስ አላችሁ መልእክት አስተላልፏል። ኢዜማ በውጤቱ በመደሰት ብቻ ሳይወሰን፣ የቀጣዮቹን ዓመታት የሥራ አቅጣጫ በግልጽ አስቀምጧል።
ለብልጽግና ፓርቲ የእንኳን ደስ አላችሁ መልእክት ያስተላለፈው ኢዜማ፤ ገዢው ፓርቲ ዴሞክራሲያዊ ተቋማትን በመገንባት፣ ፍትሐዊ የፖለቲካ ምህዳርን በመፍጠር፣ አማራጭ ሀሳቦችን በመቀበል እና ትችቶችን በሆደ ሰፊነት በማስተናገድ ኃላፊነቱን እንዲወጣ ጥሪ አቅርቧል።
Sponsored by
Surafel
2 months ago
ኢዜማ 86 መቀመጫዎችን በማግኘት በሀገር አቀፍ ደረጃ ቀዳሚው ተፎካካሪ ፓርቲ ሆኖ ማጠናቀቁን አስታወቀ
*******************
የሀገር አቀፉ ምርጫ 2018 ውጤት ይፋ መሆኑን ተከትሎ ከኢዜማ የተሠጠ መግለጫ!!
ሀገር አቀፉ ምርጫ 2018 መጠናቀቁን በትላንትናው ዕለት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ይፋዊ የምርጫ ውጤት በማሣወቅ አረጋግጧል፤ ምርጫው ከነእንከኖቹም ቢሆን በሰላም በመጠናቀቁ ፓርቲያችን እንኳን ደስ አለን ለማለት ይወዳል።
በተጨማሪም ፓርቲያችን ለውድድር በቀረበባቸው ቦታዎች 13 የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እና 73 የክልል እና የከተማ ምክር ቤት ወንበሮችን በድምሩ 86 መቀመጫዎችን በማግኘት በሀገር አቀፍ ደረጃ ቀዳሚው ተፎካካሪ ፓርቲ ሆኖ አጠናቋል። ይህንን ተጨባጭ ስኬት ላስመዘገቡ የፓርቲያችን ዕጩዎች፣ አባላት፣ ደጋፊዎች እና በሂደቱ በቅንነት ለተሳተፉ አካላት ሁሉ እንኳን ደስ አለን እንኳን ደስ አላችሁ ለማለት ይወዳል።
ፓርቲያችን ከቀጣዩ ምርጫ በፊት ባሉት ዓመታት ጠንካራ ጎኖቹን በማስቀጠል እንዲሁም የነበሩበትን ክፍተቶች በስትራቴጂ እና ሌሎች አስፈላጊ ተግባራት በመሙላት ተጨባጭ የተፎካካሪ ፓርቲነት ሚናውን ጊዜ ሳያባክን የሚጀምረው ዛሬ መሆኑን እየገለፅን፤ በነዚህ ዓመታት ከዚህ ቀደም ስናደርገው እንደነበረ ሁሉ ብሔራዊ ጥቅሞችን በሚያሣኩ ጉዳዮች ከሁሉም ኢትዮጵያዊ ኃይል ጋር በመተባበር የምንንቀሳቀስበት መፎካከሪያ አጀንዳዎች ላይ ማኅበረሰባችንን በሚመጥን ጨዋነት ልዩነቶቻችንን እና ትችቶቻችንን እያቀረብን የጀመርነውን ጤናማና ዘመናዊ የፖለቲካ ባሕል የማዋለድ ተግባራችንን በተጠናከረ መልኩ የምንቀጥልበት እንዲሁም ለተጨማሪ ስኬት የምንንደረደርበት እንደሚሆን ቃል እንገባለን።
በመጨረሻም ገዢ ሆኖ እንዲቀጥል ለተመረጠው ብልጽግና ፓርቲ እንዲሁም በውድድሩ ተሳትፋችሁ የሕዝብ ውክልናን ላሳካችሁ ተፎካካሪዎች እንኳን ደስ አላችሁ ለማለት እንወዳለን።
አሸናፊው ፓርቲ ከዛሬ ጀምሮ ዴሞክራሲያዊ ተቋማትን ለመገንባትና ፍትሐዊ የፖለቲካ ምህዳርን ለሁሉም እኩል ተደራሽ ለማድረግ በቁርጠኝነት እንዲሠራ፤ ለሀገር እድገትና ለውጥ ጠቃሚ ሀሳቦች ከማንኛውም ወገን ሊገኙ እንደሚችሉ በመረዳት አማራጭ ሃሳቦችን እንዲሰማ፤ እንዲሁም ትችቶችን በሆደ ሰፊነት እያስተናገደ ሀገራችን የሚያስፈልጋትን ዴሞክራሲ በጋራ እንድንገነባ ጥሪ እናቀርባለን።
Ethiopian Broadcasting Corporation #ምርጫ #ኢዜማ #ኢትዮጵያ
*******************
የሀገር አቀፉ ምርጫ 2018 ውጤት ይፋ መሆኑን ተከትሎ ከኢዜማ የተሠጠ መግለጫ!!
ሀገር አቀፉ ምርጫ 2018 መጠናቀቁን በትላንትናው ዕለት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ይፋዊ የምርጫ ውጤት በማሣወቅ አረጋግጧል፤ ምርጫው ከነእንከኖቹም ቢሆን በሰላም በመጠናቀቁ ፓርቲያችን እንኳን ደስ አለን ለማለት ይወዳል።
በተጨማሪም ፓርቲያችን ለውድድር በቀረበባቸው ቦታዎች 13 የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እና 73 የክልል እና የከተማ ምክር ቤት ወንበሮችን በድምሩ 86 መቀመጫዎችን በማግኘት በሀገር አቀፍ ደረጃ ቀዳሚው ተፎካካሪ ፓርቲ ሆኖ አጠናቋል። ይህንን ተጨባጭ ስኬት ላስመዘገቡ የፓርቲያችን ዕጩዎች፣ አባላት፣ ደጋፊዎች እና በሂደቱ በቅንነት ለተሳተፉ አካላት ሁሉ እንኳን ደስ አለን እንኳን ደስ አላችሁ ለማለት ይወዳል።
ፓርቲያችን ከቀጣዩ ምርጫ በፊት ባሉት ዓመታት ጠንካራ ጎኖቹን በማስቀጠል እንዲሁም የነበሩበትን ክፍተቶች በስትራቴጂ እና ሌሎች አስፈላጊ ተግባራት በመሙላት ተጨባጭ የተፎካካሪ ፓርቲነት ሚናውን ጊዜ ሳያባክን የሚጀምረው ዛሬ መሆኑን እየገለፅን፤ በነዚህ ዓመታት ከዚህ ቀደም ስናደርገው እንደነበረ ሁሉ ብሔራዊ ጥቅሞችን በሚያሣኩ ጉዳዮች ከሁሉም ኢትዮጵያዊ ኃይል ጋር በመተባበር የምንንቀሳቀስበት መፎካከሪያ አጀንዳዎች ላይ ማኅበረሰባችንን በሚመጥን ጨዋነት ልዩነቶቻችንን እና ትችቶቻችንን እያቀረብን የጀመርነውን ጤናማና ዘመናዊ የፖለቲካ ባሕል የማዋለድ ተግባራችንን በተጠናከረ መልኩ የምንቀጥልበት እንዲሁም ለተጨማሪ ስኬት የምንንደረደርበት እንደሚሆን ቃል እንገባለን።
በመጨረሻም ገዢ ሆኖ እንዲቀጥል ለተመረጠው ብልጽግና ፓርቲ እንዲሁም በውድድሩ ተሳትፋችሁ የሕዝብ ውክልናን ላሳካችሁ ተፎካካሪዎች እንኳን ደስ አላችሁ ለማለት እንወዳለን።
አሸናፊው ፓርቲ ከዛሬ ጀምሮ ዴሞክራሲያዊ ተቋማትን ለመገንባትና ፍትሐዊ የፖለቲካ ምህዳርን ለሁሉም እኩል ተደራሽ ለማድረግ በቁርጠኝነት እንዲሠራ፤ ለሀገር እድገትና ለውጥ ጠቃሚ ሀሳቦች ከማንኛውም ወገን ሊገኙ እንደሚችሉ በመረዳት አማራጭ ሃሳቦችን እንዲሰማ፤ እንዲሁም ትችቶችን በሆደ ሰፊነት እያስተናገደ ሀገራችን የሚያስፈልጋትን ዴሞክራሲ በጋራ እንድንገነባ ጥሪ እናቀርባለን።
Ethiopian Broadcasting Corporation #ምርጫ #ኢዜማ #ኢትዮጵያ
2 months ago
ብልጽግና ፓርቲ አሸነፈ!
- የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ
#ethiopia | አዲስ አበባ – የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዛሬ ይፋ ባደረገው የምርጫ ውጤት መሠረት፣ ገዥው ብልጽግና ፓርቲ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ምርጫ ከፍተኛ ድል አስመዝግቧል።
የምርጫ ቦርዱ ሰብሳቢ ወይዘሮ መላትወርቅ ኃይሉ እንዳስታወቁት፣ ብልጽግና ፓርቲ ውድድር ከተካሄደባቸው 486 የፓርላማ መቀመጫዎች ውስጥ 438 መቀመጫዎችን በማሸነፍ ከፍተኛ አብላጫ አግኝቷል።
ምርጫው ሰኔ 1 ቀን ቢካሄድም፣ በትግራይ፣ በአማራ እና በኦሮሚያ ክልሎች የሚገኙ አንዳንድ አካባቢዎች በጸጥታ ችግሮች ምክንያት ምርጫው ሳይካሄድ ቀርቷል።
በሌሎች የአገሪቱ ክፍሎች ግን በታቀደው የጊዜ ሰሌዳ መሠረት ተከናውኗል።
በምርጫው ከ40 በላይ ፓርቲዎች ቢሳተፉም፣ ብዙዎቹ በፋይናንስ እጥረት ምክንያት ሰፊ ተሳትፎ ማድረግ አልቻሉም። በ64 የምርጫ ክልሎች ውስጥም ብልጽግና ፓርቲ ያለ ተቀናቃኝ ለብቻው ተወዳድሯል።
ከተፎካካሪ ፓርቲዎች ውስጥ ኢዜማ 293 ዕጩዎችን ለውድድር ያቀረበ ሲሆን፣ ብልጽግና ፓርቲ 461 ዕጩዎችን አቅርቦ ነበር። የምርጫ ቦርዱ እንደገለጸው፣ የብልጽግና ፓርቲ ድል ውድድር ከተካሄደባቸው መቀመጫዎች 90 በመቶ የሚጠጋውን ይሸፍናል።
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጠቅላይ ሚኒስትሩን የሚሰይም በመሆኑ፣ ይህ ውጤት ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ በስልጣን ላይ ለተጨማሪ አምስት ዓመታት የሚቆዩበትን እድል እንደሚያሰፋ ተገልጿል።
በሌላ በኩል፣ አንዳንድ የፖለቲካ ተንታኞች በተወሰኑ የአማራ፣ የኦሮሚያ እና የትግራይ አካባቢዎች ምርጫው አለመካሄዱ በአገሪቱ ውስጥ ያሉ የፀጥታና የፖለቲካ ችግሮች አሁንም ቀጣይነት እንዳላቸው የሚያሳይ መሆኑን ገልጸዋል።
– የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ
- የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ
#ethiopia | አዲስ አበባ – የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዛሬ ይፋ ባደረገው የምርጫ ውጤት መሠረት፣ ገዥው ብልጽግና ፓርቲ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ምርጫ ከፍተኛ ድል አስመዝግቧል።
የምርጫ ቦርዱ ሰብሳቢ ወይዘሮ መላትወርቅ ኃይሉ እንዳስታወቁት፣ ብልጽግና ፓርቲ ውድድር ከተካሄደባቸው 486 የፓርላማ መቀመጫዎች ውስጥ 438 መቀመጫዎችን በማሸነፍ ከፍተኛ አብላጫ አግኝቷል።
ምርጫው ሰኔ 1 ቀን ቢካሄድም፣ በትግራይ፣ በአማራ እና በኦሮሚያ ክልሎች የሚገኙ አንዳንድ አካባቢዎች በጸጥታ ችግሮች ምክንያት ምርጫው ሳይካሄድ ቀርቷል።
በሌሎች የአገሪቱ ክፍሎች ግን በታቀደው የጊዜ ሰሌዳ መሠረት ተከናውኗል።
በምርጫው ከ40 በላይ ፓርቲዎች ቢሳተፉም፣ ብዙዎቹ በፋይናንስ እጥረት ምክንያት ሰፊ ተሳትፎ ማድረግ አልቻሉም። በ64 የምርጫ ክልሎች ውስጥም ብልጽግና ፓርቲ ያለ ተቀናቃኝ ለብቻው ተወዳድሯል።
ከተፎካካሪ ፓርቲዎች ውስጥ ኢዜማ 293 ዕጩዎችን ለውድድር ያቀረበ ሲሆን፣ ብልጽግና ፓርቲ 461 ዕጩዎችን አቅርቦ ነበር። የምርጫ ቦርዱ እንደገለጸው፣ የብልጽግና ፓርቲ ድል ውድድር ከተካሄደባቸው መቀመጫዎች 90 በመቶ የሚጠጋውን ይሸፍናል።
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጠቅላይ ሚኒስትሩን የሚሰይም በመሆኑ፣ ይህ ውጤት ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ በስልጣን ላይ ለተጨማሪ አምስት ዓመታት የሚቆዩበትን እድል እንደሚያሰፋ ተገልጿል።
በሌላ በኩል፣ አንዳንድ የፖለቲካ ተንታኞች በተወሰኑ የአማራ፣ የኦሮሚያ እና የትግራይ አካባቢዎች ምርጫው አለመካሄዱ በአገሪቱ ውስጥ ያሉ የፀጥታና የፖለቲካ ችግሮች አሁንም ቀጣይነት እንዳላቸው የሚያሳይ መሆኑን ገልጸዋል።
– የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ
2 months ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዛሬ እሁድ ዕለት ይፋ ባደረገው የምርጫ ውጤት መሠረት፣ የጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ብልጽግና ፓርቲ ከፍተኛ አብላጫ ድምፅ በማግኘት አሸንፏል።
የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ወይዘሮ ሜላትወርቅ ኃይሉ እንዳስታወቁት "ገዥው ብልጽግና ፓርቲ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ውድድር ከተካሄደባቸው 486 መቀመጫዎች ውስጥ 438ቱን አሸንፏል"።
ሰኔ አንድ ቀን የተካሄደው ይኸው የፓርላማ ምርጫ፣ በትግራይ፣ በአማራ እና በኦሮሚያ ክልሎች ውስጥ በሚገኙ አንዳንድ አካባቢዎችን ጨምሮ በተወሰኑ የሀገሪቱ ክፍሎች ሳይካሄድ ቢቀርም፣ በተቀረው የሀገሪቱ ክፍል ግን በተያዘለት መርሃ ግብር መሰረት ተከናውኗል።
ከጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ የብልጽግና ፓርቲ ጋር ከ40 በላይ ፓርቲዎች የተወዳደሩ ቢሆንም፣ አብዛኛዎቹ የፋይናንስ እጥረት የነበረባቸው በመሆኑ ገዥው ፓርቲ በ64 የምርጫ ክልሎች ውስጥ ያለ ምንም ተቀናቃኝ ለብቻው ተወዳድሯል። ከተፎካካሪ ፓርቲዎች በተሻለ ከፍተኛ የዕጩዎች ውክልና የነበረው ኢዜማ 293 ዕጩዎችን ሲያቀርብ፣ ብልጽግና ፓርቲ በበኩሉ 461 ዕጩዎችን ለውድድር አቅርቦ ነበር።
"የብልጽግና ፓርቲ ድል ውድድር ከተካሄደባቸው መቀመጫዎች ውስጥ ወደ 90 በመቶ የሚጠጋውን ይሸፍናል" ሲል የምርጫ ቦርድ በመግለጫው አብራርቷል።
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት (ፓርላማው) ጠቅላይ ሚኒስትሩን የሚሰይም በመሆኑ፣ ይህ አብላጫ የምርጫ ውጤት እ.ኤ.አ ከ2018 ጀምሮ በስልጣን ላይ ላሉት አብይ አህመድ ሀገሪቱን ለተጨማሪ አምስት ዓመታት በቢሮ ሆነው እንዲመሩ ሰፊ ዕድል የሚሰጣቸው ይሆናል።
ይሁን እንጂ አንዳንድ የፖለቲካ ተንታኞች በአማራ፣ በኦሮሚያ እና በትግራይ የተወሰኑ አካባቢዎች ምርጫው ሳይካሄድ መታገዱ፣ እስካሁን እልባት ያላገኙ የውስጥ ግጭቶች በሀገሪቱ ፖለቲካዊ እንቅስቃሴ ላይ እያሳደሩ ያለውን ከፍተኛ ጫና በጉልህ የሚያሳይ ነው ሲሉ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።
የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ወይዘሮ ሜላትወርቅ ኃይሉ እንዳስታወቁት "ገዥው ብልጽግና ፓርቲ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ውድድር ከተካሄደባቸው 486 መቀመጫዎች ውስጥ 438ቱን አሸንፏል"።
ሰኔ አንድ ቀን የተካሄደው ይኸው የፓርላማ ምርጫ፣ በትግራይ፣ በአማራ እና በኦሮሚያ ክልሎች ውስጥ በሚገኙ አንዳንድ አካባቢዎችን ጨምሮ በተወሰኑ የሀገሪቱ ክፍሎች ሳይካሄድ ቢቀርም፣ በተቀረው የሀገሪቱ ክፍል ግን በተያዘለት መርሃ ግብር መሰረት ተከናውኗል።
ከጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ የብልጽግና ፓርቲ ጋር ከ40 በላይ ፓርቲዎች የተወዳደሩ ቢሆንም፣ አብዛኛዎቹ የፋይናንስ እጥረት የነበረባቸው በመሆኑ ገዥው ፓርቲ በ64 የምርጫ ክልሎች ውስጥ ያለ ምንም ተቀናቃኝ ለብቻው ተወዳድሯል። ከተፎካካሪ ፓርቲዎች በተሻለ ከፍተኛ የዕጩዎች ውክልና የነበረው ኢዜማ 293 ዕጩዎችን ሲያቀርብ፣ ብልጽግና ፓርቲ በበኩሉ 461 ዕጩዎችን ለውድድር አቅርቦ ነበር።
"የብልጽግና ፓርቲ ድል ውድድር ከተካሄደባቸው መቀመጫዎች ውስጥ ወደ 90 በመቶ የሚጠጋውን ይሸፍናል" ሲል የምርጫ ቦርድ በመግለጫው አብራርቷል።
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት (ፓርላማው) ጠቅላይ ሚኒስትሩን የሚሰይም በመሆኑ፣ ይህ አብላጫ የምርጫ ውጤት እ.ኤ.አ ከ2018 ጀምሮ በስልጣን ላይ ላሉት አብይ አህመድ ሀገሪቱን ለተጨማሪ አምስት ዓመታት በቢሮ ሆነው እንዲመሩ ሰፊ ዕድል የሚሰጣቸው ይሆናል።
ይሁን እንጂ አንዳንድ የፖለቲካ ተንታኞች በአማራ፣ በኦሮሚያ እና በትግራይ የተወሰኑ አካባቢዎች ምርጫው ሳይካሄድ መታገዱ፣ እስካሁን እልባት ያላገኙ የውስጥ ግጭቶች በሀገሪቱ ፖለቲካዊ እንቅስቃሴ ላይ እያሳደሩ ያለውን ከፍተኛ ጫና በጉልህ የሚያሳይ ነው ሲሉ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።
2 months ago
የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የክልል ምክር ቤት ውጤት
👉ሀረሪ ክልል - የክልል ምክር ቤት መቀመጫ ብዛት 36
ብልጽግና ፓርቲ - 32 መቀመጫዎች
የኢትዮጵያ ብሔራዊ አንድነት ፓርቲ - 1 መቀመጫ
ነጻነት እና እኩልነት ፓርቲ - 1 መቀመጫ
የሐረር ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ - 1 መቀመጫ
የግል ተወዳዳሪው ጀማል አባገሮ አሕመድ - 1 መቀመጫ
👉ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል - የክልል ምክር ቤት መቀመጫ ብዛት 170
ብልጽግና ፓርቲ - 143 መቀመጫዎች
ኢዜማ - 12 መቀመጫዎች
ነጻነት እና እኩልነት ፓርቲ - 7 መቀመጫዎች
ትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት - 3 መቀመጫዎች
ጎጎት ለጉራጌ አንድነት እና ፍትሕ ፓርቲ - 3 መቀመጫዎች
የወሎ ሕዝቦች ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ - 1 መቀመጫ
የወለኔ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ - 1 መቀመጫ
👉ሲዳማ ክልል - የክልል ምክር ቤት መቀመጫ ብዛት 190
ብልጽግና ፓርቲ - 175 መቀመጫዎች
የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዴሞክራሲያዊ አንድነት መድረክ - 8 መቀመጫዎች
ሲዳማ አንድነት ፓርቲ - 3 መቀመጫዎች
የሲዳማ ሕዝብ አንድነት ዴሞክራሲያዊ ድርጅት - 1 መቀመጫ
ባልደራስ ለእውነተኛ ዴሞክራሲ - 1 መቀመጫ
የኢትዮጵያ ዴሞክራቲክ ሕብረት - 1 መቀመጫ
የመላው ሲዳማ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ አንድነት ፓርቲ - 1 መቀመጫ
👉ሀረሪ ክልል - የክልል ምክር ቤት መቀመጫ ብዛት 36
ብልጽግና ፓርቲ - 32 መቀመጫዎች
የኢትዮጵያ ብሔራዊ አንድነት ፓርቲ - 1 መቀመጫ
ነጻነት እና እኩልነት ፓርቲ - 1 መቀመጫ
የሐረር ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ - 1 መቀመጫ
የግል ተወዳዳሪው ጀማል አባገሮ አሕመድ - 1 መቀመጫ
👉ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል - የክልል ምክር ቤት መቀመጫ ብዛት 170
ብልጽግና ፓርቲ - 143 መቀመጫዎች
ኢዜማ - 12 መቀመጫዎች
ነጻነት እና እኩልነት ፓርቲ - 7 መቀመጫዎች
ትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት - 3 መቀመጫዎች
ጎጎት ለጉራጌ አንድነት እና ፍትሕ ፓርቲ - 3 መቀመጫዎች
የወሎ ሕዝቦች ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ - 1 መቀመጫ
የወለኔ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ - 1 መቀመጫ
👉ሲዳማ ክልል - የክልል ምክር ቤት መቀመጫ ብዛት 190
ብልጽግና ፓርቲ - 175 መቀመጫዎች
የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዴሞክራሲያዊ አንድነት መድረክ - 8 መቀመጫዎች
ሲዳማ አንድነት ፓርቲ - 3 መቀመጫዎች
የሲዳማ ሕዝብ አንድነት ዴሞክራሲያዊ ድርጅት - 1 መቀመጫ
ባልደራስ ለእውነተኛ ዴሞክራሲ - 1 መቀመጫ
የኢትዮጵያ ዴሞክራቲክ ሕብረት - 1 መቀመጫ
የመላው ሲዳማ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ አንድነት ፓርቲ - 1 መቀመጫ
2 months ago
ጠቅላይ ሚኒስትሩ እና ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በተወዳደሩበት ምርጫ ክልሎች አሸነፉ።
ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ለፓርላማ በተወዳደሩበት ምርጫ ክልል ማሸነፋቸውን ምርጫ ቦርድ ይፋ አድርጓል።
ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ በኦሮሚያ ክልል ለፓርላማ በተወዳደሩበት ጎማ ሁለት ምርጫ ክልል ማሸነፋቸውን ዛሬ ምሽት ምርጫ ቦርድ ይፋ አድርጓል።
በምርጫ ክልሉ ብልጽግና ፓርቲ፣የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ ፓርቲ ኢዜማ እና ነጻነት እና እኩልነት ፓርቲ ተወዳድረው ነበር።
በክልሉ ከፍተኛ ድምጽ ያገኘው በልጽግና ነው ።
በተጨማሪም በአማራ ክልል ባህርዳር ከተማ ምርጫ ክልል ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ተመስገን ጥሩነህ አሸንፈዋል ብሏል ምርጫ ቦርድ።
Seledadotio
Seledadotio
ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ለፓርላማ በተወዳደሩበት ምርጫ ክልል ማሸነፋቸውን ምርጫ ቦርድ ይፋ አድርጓል።
ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ በኦሮሚያ ክልል ለፓርላማ በተወዳደሩበት ጎማ ሁለት ምርጫ ክልል ማሸነፋቸውን ዛሬ ምሽት ምርጫ ቦርድ ይፋ አድርጓል።
በምርጫ ክልሉ ብልጽግና ፓርቲ፣የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ ፓርቲ ኢዜማ እና ነጻነት እና እኩልነት ፓርቲ ተወዳድረው ነበር።
በክልሉ ከፍተኛ ድምጽ ያገኘው በልጽግና ነው ።
በተጨማሪም በአማራ ክልል ባህርዳር ከተማ ምርጫ ክልል ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ተመስገን ጥሩነህ አሸንፈዋል ብሏል ምርጫ ቦርድ።
Seledadotio
Seledadotio
2 months ago
ጠቅላይ ሚኒስትሩ እና ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በተወዳደሩበት ምርጫ ክልሎች አሸነፉ።
ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ለፓርላማ በተወዳደሩበት ምርጫ ክልል ማሸነፋቸውን ምርጫ ቦርድ ይፋ አድርጓል።
ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ በኦሮሚያ ክልል ለፓርላማ በተወዳደሩበት ጎማ ሁለት ምርጫ ክልል ማሸነፋቸውን ዛሬ ምሽት ምርጫ ቦርድ ይፋ አድርጓል።
በምርጫ ክልሉ ብልጽግና ፓርቲ፣የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ ፓርቲ ኢዜማ እና ነጻነት እና እኩልነት ፓርቲ ተወዳድረው ነበር።
በክልሉ ከፍተኛ ድምጽ ያገኘው በልጽግና ነው ።
በተጨማሪም በአማራ ክልል ባህርዳር ከተማ ምርጫ ክልል ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ተመስገን ጥሩነህ አሸንፈዋል ብሏል ምርጫ ቦርድ።
ዘገባው የሸገር ሬዲዮ ነው
ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ለፓርላማ በተወዳደሩበት ምርጫ ክልል ማሸነፋቸውን ምርጫ ቦርድ ይፋ አድርጓል።
ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ በኦሮሚያ ክልል ለፓርላማ በተወዳደሩበት ጎማ ሁለት ምርጫ ክልል ማሸነፋቸውን ዛሬ ምሽት ምርጫ ቦርድ ይፋ አድርጓል።
በምርጫ ክልሉ ብልጽግና ፓርቲ፣የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ ፓርቲ ኢዜማ እና ነጻነት እና እኩልነት ፓርቲ ተወዳድረው ነበር።
በክልሉ ከፍተኛ ድምጽ ያገኘው በልጽግና ነው ።
በተጨማሪም በአማራ ክልል ባህርዳር ከተማ ምርጫ ክልል ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ተመስገን ጥሩነህ አሸንፈዋል ብሏል ምርጫ ቦርድ።
ዘገባው የሸገር ሬዲዮ ነው
2 months ago
በ25 ድምፅ ወደ ምክር ቤት፤ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ እጅግ ዝቅተኛ በሆነ የድምፅ ቁጥር የተመረጡ ተፎካካሪ ዕጩዎች መኖራቸው ታወቀ!
ምርጫ ቦርድ ባወጣቸው ተከታታይ መግለጫዎች ያጸደቃቸው ከፊል ውጤቶች፣ በርካታ ተፎካካሪ በሌለባቸው የምርጫ ክልሎች የሚወዳደሩ የተቃዋሚ ዕጩዎች እጅግ ዝቅተኛ በሆነ የመራጮች ድምፅ ወደ ምክር ቤቶች መግባታቸውን አሳይተዋል።
ከእነዚህ መካከል ለድሬዳዋ ከተማ ምክር ቤት በኩርቱ የምርጫ ክልል የተመረጡት የነፃነትና እኩልነት ፓርቲ ዕጩ አቶ ጀማል ኡመር ኢብራሂም፣ ከተመዘገቡት 2,204 መራጮች መካከል ያገኙት ድምፅ 25 ብቻ (1% ገደማ) እንደሆነ ተገልጿል።
በጀሎበጂና የምርጫ ክልልም የአዲስ ትውልድ ፓርቲ ተወካዩ አቶ ረመዳን መሐመድ ሰኢድ 200 ድምፅ (3%) ብቻ በማግኘት ወደ ምክር ቤት መግባት ችለዋል።ለዚህም ዋነኛው ምክንያት በእነዚህ የምርጫ ክልሎች ከወንበሮቹ ቁጥር እኩል ከሆኑት ዕጩዎች ውጪ ሌላ ተወዳዳሪ ፓርቲ ባለመኖሩ ነው።
እስካሁን ከተመረጡት 8 ተቃዋሚዎች መካከል እውነተኛ የአብላጫ ድምፅ (ከ50% በላይ) ያገኙት የኦብነግ ተወካይ አቶ መሀሙድ ሀሰን (73%) እና የአብን ዕጩ አቶ ጣሂር መሀመድ (59%) ብቻ ሲሆኑ፣ ቀሪዎቹ 6ቱ ዕጩዎች የኢዜማውን መሪ አቶ እዮብ መሳፍንትን (42%) ጨምሮ ከ50% በታች ድምፅ አግኝተዋል።ስምንቱም የተቃዋሚ ወኪሎች ያሸነፏቸው ወንበሮች ብልፅግና ፓርቲ ውክልናን ለማሳደግ በሚል ሆነ ብሎ ዕጩ ያላቀረበባቸው መሆኑ ታውቋል።
ኢትዮጵያ ኢንሳይደር
Seledadotio
Seledadotio
ምርጫ ቦርድ ባወጣቸው ተከታታይ መግለጫዎች ያጸደቃቸው ከፊል ውጤቶች፣ በርካታ ተፎካካሪ በሌለባቸው የምርጫ ክልሎች የሚወዳደሩ የተቃዋሚ ዕጩዎች እጅግ ዝቅተኛ በሆነ የመራጮች ድምፅ ወደ ምክር ቤቶች መግባታቸውን አሳይተዋል።
ከእነዚህ መካከል ለድሬዳዋ ከተማ ምክር ቤት በኩርቱ የምርጫ ክልል የተመረጡት የነፃነትና እኩልነት ፓርቲ ዕጩ አቶ ጀማል ኡመር ኢብራሂም፣ ከተመዘገቡት 2,204 መራጮች መካከል ያገኙት ድምፅ 25 ብቻ (1% ገደማ) እንደሆነ ተገልጿል።
በጀሎበጂና የምርጫ ክልልም የአዲስ ትውልድ ፓርቲ ተወካዩ አቶ ረመዳን መሐመድ ሰኢድ 200 ድምፅ (3%) ብቻ በማግኘት ወደ ምክር ቤት መግባት ችለዋል።ለዚህም ዋነኛው ምክንያት በእነዚህ የምርጫ ክልሎች ከወንበሮቹ ቁጥር እኩል ከሆኑት ዕጩዎች ውጪ ሌላ ተወዳዳሪ ፓርቲ ባለመኖሩ ነው።
እስካሁን ከተመረጡት 8 ተቃዋሚዎች መካከል እውነተኛ የአብላጫ ድምፅ (ከ50% በላይ) ያገኙት የኦብነግ ተወካይ አቶ መሀሙድ ሀሰን (73%) እና የአብን ዕጩ አቶ ጣሂር መሀመድ (59%) ብቻ ሲሆኑ፣ ቀሪዎቹ 6ቱ ዕጩዎች የኢዜማውን መሪ አቶ እዮብ መሳፍንትን (42%) ጨምሮ ከ50% በታች ድምፅ አግኝተዋል።ስምንቱም የተቃዋሚ ወኪሎች ያሸነፏቸው ወንበሮች ብልፅግና ፓርቲ ውክልናን ለማሳደግ በሚል ሆነ ብሎ ዕጩ ያላቀረበባቸው መሆኑ ታውቋል።
ኢትዮጵያ ኢንሳይደር
Seledadotio
Seledadotio
2 months ago
በህወሓት ላይ እርምጃ ይወሰድ-ኢዜማ‼️
የፌዴራል መንግሥቱ ሕውሓት ላይ እርምጃ እንዲወስድ ኢዜማ ጠየቀ‼️
አካሄዱ ‹መኢሶንን ይመስላል› በሚል የሚተቸው ኢዜማ በትግራይ ያንዣበበውን ወታደራዊ ውጥረት በተመለከተ መግለጫ አውጥቷል፡፡ የፌዴራል መንግስቱ ሕውሓት ላይ እርምጃ እንዲወስድም ጠይቋል፡፡ ሕውሓት ደርግን ጥሎ ስልጣን ከተቆጣጠረ አንስቶ የሰራቸውን ጥፋቶች የሚዘረዝረው መግለጫው፤ አሁን ላለው አገራዊ ችግር መንስኤው ሕውሓት ያሠፈነው የብሔር ፖለቲካ እንደሆነ አንስቷል፡፡
ለፕሪቶሪያ ስምምነት አለመተግበር እና ለተፈናቃዮች አለመመለስ ሕውሓትን ብቻ ተጠያቂ ያደገው የፓርቲው መግለጫ፤ ‹‹ይህንን ኃይል በቃህ ማለት እና በትግራይ ያሉ ወገኖቻችንን ከማያባራ መከራ መታደግ የሁላችንም ኢትዮጵያውያን የጋራ የቤት ሥራ ሊሆን ይገባል፤ ጦርነትን ሳይጀመር በፊት ማስቆም ይገባናል›› ሲል ጠይቋል፡፡
‹‹እንደ ሕወሓት ዓይነት ደም የማይጠረቃ አካል እና እሱን የሚዘውሩ ጥቂት ግለሰቦች በቃችሁ ብሎ ለማስቆም እና የትግራይ ህዝብን ካላስፈላጊ መከራ ለመታደግ በህዝብ ላይ ምንም አይነት መስዋዕትነት በማያስከትል መልኩ በሕገወጥ ቡድኑ ላይ ብቻ ያነጣጠረ አስፈላጊ ሕጋዊ እርምጃ በመንግሥት እና ከመንግሥት ጋር በጋራ በሚቆሙ ማንኛውም ለትግራይ ማኅበረሰብ በሚቆረቆር አካል ሊወሰድ እንደሚገባ ያምናል›› በማለት ሕውሃት ላይ እርምጃ እንዲወሰድ ጠይቋል፡፡
Seledadotio
Seledadotio
የፌዴራል መንግሥቱ ሕውሓት ላይ እርምጃ እንዲወስድ ኢዜማ ጠየቀ‼️
አካሄዱ ‹መኢሶንን ይመስላል› በሚል የሚተቸው ኢዜማ በትግራይ ያንዣበበውን ወታደራዊ ውጥረት በተመለከተ መግለጫ አውጥቷል፡፡ የፌዴራል መንግስቱ ሕውሓት ላይ እርምጃ እንዲወስድም ጠይቋል፡፡ ሕውሓት ደርግን ጥሎ ስልጣን ከተቆጣጠረ አንስቶ የሰራቸውን ጥፋቶች የሚዘረዝረው መግለጫው፤ አሁን ላለው አገራዊ ችግር መንስኤው ሕውሓት ያሠፈነው የብሔር ፖለቲካ እንደሆነ አንስቷል፡፡
ለፕሪቶሪያ ስምምነት አለመተግበር እና ለተፈናቃዮች አለመመለስ ሕውሓትን ብቻ ተጠያቂ ያደገው የፓርቲው መግለጫ፤ ‹‹ይህንን ኃይል በቃህ ማለት እና በትግራይ ያሉ ወገኖቻችንን ከማያባራ መከራ መታደግ የሁላችንም ኢትዮጵያውያን የጋራ የቤት ሥራ ሊሆን ይገባል፤ ጦርነትን ሳይጀመር በፊት ማስቆም ይገባናል›› ሲል ጠይቋል፡፡
‹‹እንደ ሕወሓት ዓይነት ደም የማይጠረቃ አካል እና እሱን የሚዘውሩ ጥቂት ግለሰቦች በቃችሁ ብሎ ለማስቆም እና የትግራይ ህዝብን ካላስፈላጊ መከራ ለመታደግ በህዝብ ላይ ምንም አይነት መስዋዕትነት በማያስከትል መልኩ በሕገወጥ ቡድኑ ላይ ብቻ ያነጣጠረ አስፈላጊ ሕጋዊ እርምጃ በመንግሥት እና ከመንግሥት ጋር በጋራ በሚቆሙ ማንኛውም ለትግራይ ማኅበረሰብ በሚቆረቆር አካል ሊወሰድ እንደሚገባ ያምናል›› በማለት ሕውሃት ላይ እርምጃ እንዲወሰድ ጠይቋል፡፡
Seledadotio
Seledadotio
2 months ago
ለኢትዮጵያ አዲስ የፖለቲካ ባህል ያመጣው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 3፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የፖለቲካ ፓርቲዎች 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ልምምድ ታሪክ የሰላማዊ ፖለቲካ ውድድር እና የሕዝብ ተሳትፎ መጠናከርን ያሳየ ነው አሉ።
በብልፅግና ፓርቲ ኦሮሚያ ክልል ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ ሞገስ ኤዴዔ እንዳሉት÷ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የኢትዮጵያን የምርጫ ታሪክና ሂደት በመቀየር በሀገሪቱ አስተማማኝና ዘመናዊ የዴሞክራሲ ሥርዓት ለመገንባት የሚያስችል አዲስ የፖለቲካ ባህል ተመዝግቧል።
ኋላ ቀርና በኃይል የመጠቀም የፖለቲካ ፉክክር ሥርዓት በመቀየር በትብብር እና በፖለቲካዊ ውድድር መርህ ላይ የተመሰረተ አዲስ አሰራር በተግባር መታየቱንም አስረድተዋል።
ሰኞ ምርጫ አከናውነን ማክሰኞ ወደ ሥራ እንገባለን ያልነውን አሳክተናል ያሉት ኃላፊው÷ ምርጫው ኢትዮጵያ አሸናፊ የሆነችበት የታሪክ ምዕራፍ ሆኖ ማለፉን አመልክተዋል።
የኢትዮጵያ ሕዝብ በነቂስ ወጥቶ በሰላማዊ መንገድ ድምፅ የመስጠት ሂደትና ያሳየው ትዕግስት በዓለም አቀፍና በውጭ ታዛቢዎች ዘንድ አድናቆትና ምስክርነት ተሰጥቶታልም ነው ያሉት።
የኢዜማ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባል የሆኑት ታሪኩ ድንበሩ በበኩላቸው÷ ባለፉት ስድስት ምርጫዎች ይስተዋሉ የነበሩ የፖለቲካ ምልክቶች፣ የሚዲያ አጠቃቀም እና የመንግሥት ተቋማት ምላሽ ሰጪነት ተግዳሮቶች በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ አለመታየታቸውን አመልክተዋል።
እንዲሁም የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤቶች በመወያየት የተፈጠሩ ችግሮች መፍትሄ ያገኙበት ልዩ ሂደት የነበረበትና የቅሬታ ሰሚ ኮሚቴዎች በቦታው ተገኝተው ፈጣን ምላሽ የሰጡበት ሁኔታ መኖሩን አንስተዋል።
በቀጣይም በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ በጋራ መስራትና የምርጫው ውጤት ሲገለጽ ውጤቱን በጸጋ በመቀበል ለሀገር ግንባታ በትብብር መስራት እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
በሶስና አለማየሁ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 3፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የፖለቲካ ፓርቲዎች 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ልምምድ ታሪክ የሰላማዊ ፖለቲካ ውድድር እና የሕዝብ ተሳትፎ መጠናከርን ያሳየ ነው አሉ።
በብልፅግና ፓርቲ ኦሮሚያ ክልል ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ ሞገስ ኤዴዔ እንዳሉት÷ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የኢትዮጵያን የምርጫ ታሪክና ሂደት በመቀየር በሀገሪቱ አስተማማኝና ዘመናዊ የዴሞክራሲ ሥርዓት ለመገንባት የሚያስችል አዲስ የፖለቲካ ባህል ተመዝግቧል።
ኋላ ቀርና በኃይል የመጠቀም የፖለቲካ ፉክክር ሥርዓት በመቀየር በትብብር እና በፖለቲካዊ ውድድር መርህ ላይ የተመሰረተ አዲስ አሰራር በተግባር መታየቱንም አስረድተዋል።
ሰኞ ምርጫ አከናውነን ማክሰኞ ወደ ሥራ እንገባለን ያልነውን አሳክተናል ያሉት ኃላፊው÷ ምርጫው ኢትዮጵያ አሸናፊ የሆነችበት የታሪክ ምዕራፍ ሆኖ ማለፉን አመልክተዋል።
የኢትዮጵያ ሕዝብ በነቂስ ወጥቶ በሰላማዊ መንገድ ድምፅ የመስጠት ሂደትና ያሳየው ትዕግስት በዓለም አቀፍና በውጭ ታዛቢዎች ዘንድ አድናቆትና ምስክርነት ተሰጥቶታልም ነው ያሉት።
የኢዜማ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባል የሆኑት ታሪኩ ድንበሩ በበኩላቸው÷ ባለፉት ስድስት ምርጫዎች ይስተዋሉ የነበሩ የፖለቲካ ምልክቶች፣ የሚዲያ አጠቃቀም እና የመንግሥት ተቋማት ምላሽ ሰጪነት ተግዳሮቶች በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ አለመታየታቸውን አመልክተዋል።
እንዲሁም የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤቶች በመወያየት የተፈጠሩ ችግሮች መፍትሄ ያገኙበት ልዩ ሂደት የነበረበትና የቅሬታ ሰሚ ኮሚቴዎች በቦታው ተገኝተው ፈጣን ምላሽ የሰጡበት ሁኔታ መኖሩን አንስተዋል።
በቀጣይም በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ በጋራ መስራትና የምርጫው ውጤት ሲገለጽ ውጤቱን በጸጋ በመቀበል ለሀገር ግንባታ በትብብር መስራት እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
በሶስና አለማየሁ
Sponsored by
Surafel
2 months ago
“ምርጫው በሰላም መጠናቀቁ በጎ ቢሆንም መዋቅራዊ ጥሰቶች ነበሩበት” - ኢዜማ
የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ (ኢዜማ) ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. የተካሄደውን 7ኛ ሀገራዊ ምርጫ አስመልክቶ የመጀመሪያ ደረጃ ግምገማዊ መግለጫ አውጥቷል።
ፓርቲው ምርጫው ከሞላ ጎደል በሰላም መጠናቀቁን፣ ከፍተኛ የመራጭ ቁጥር መመዝገቡንና የኦንላይን አሰራር መጀመሩን እንደ በጎ ጅምር ወስዷል።
በሌላ በኩል፣ በሂደቱ ላይ የታዩ በርካታ መዋቅራዊ ተግዳሮቶችንም ወቅሷል። ገዢው ፓርቲ የመንግሥት የልማት ፕሮግራሞችን እና የሚዲያ አቅምን ለምርጫ ቅስቀሳ መጠቀሙን፣ እንዲሁም የካድሬዎችና የጸጥታ አካላት በምርጫ ጣቢያዎች ጣልቃ በመግባት በመራጮችና በተቃዋሚ ታዛቢዎች ላይ ጫና ማድረጋቸውን ገልጿል።
በተጨማሪም የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አስፈጻሚዎች ገለልተኝነት ማጣት፣ የተፎካካሪ ፓርቲዎች የተሟላ ታዛቢ አለማሰማራት እና የሲቪክ ማኅበራት ደካማ ተሳትፎ በምርጫው ላይ ክፍተት መፍጠራቸውን አብራርቷል።
ዓለም አቀፍ ሚዲያዎችም የራሳቸውን ፍላጎት አስቀድመው ሂደቱን ሲያጣጥሉ እንደነበር ጠቁሟል።
ኢዜማ በስተመጨረሻም፣ ያሉትን ውስብስብ ችግሮች ተጋፍጦ የተሻለ ስኬት ማስመዝገቡን ጠቅሶ፣ ሥልጣን መያዝ የሚቻለው በሰላማዊ መንገድ ብቻ በመሆኑ በቀጣይም ለዲሞክራሲ ግንባታ በቁርጠኝነት እንደሚሠራ አስታውቋል።
Seledadotio
Seledadotio
የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ (ኢዜማ) ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. የተካሄደውን 7ኛ ሀገራዊ ምርጫ አስመልክቶ የመጀመሪያ ደረጃ ግምገማዊ መግለጫ አውጥቷል።
ፓርቲው ምርጫው ከሞላ ጎደል በሰላም መጠናቀቁን፣ ከፍተኛ የመራጭ ቁጥር መመዝገቡንና የኦንላይን አሰራር መጀመሩን እንደ በጎ ጅምር ወስዷል።
በሌላ በኩል፣ በሂደቱ ላይ የታዩ በርካታ መዋቅራዊ ተግዳሮቶችንም ወቅሷል። ገዢው ፓርቲ የመንግሥት የልማት ፕሮግራሞችን እና የሚዲያ አቅምን ለምርጫ ቅስቀሳ መጠቀሙን፣ እንዲሁም የካድሬዎችና የጸጥታ አካላት በምርጫ ጣቢያዎች ጣልቃ በመግባት በመራጮችና በተቃዋሚ ታዛቢዎች ላይ ጫና ማድረጋቸውን ገልጿል።
በተጨማሪም የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አስፈጻሚዎች ገለልተኝነት ማጣት፣ የተፎካካሪ ፓርቲዎች የተሟላ ታዛቢ አለማሰማራት እና የሲቪክ ማኅበራት ደካማ ተሳትፎ በምርጫው ላይ ክፍተት መፍጠራቸውን አብራርቷል።
ዓለም አቀፍ ሚዲያዎችም የራሳቸውን ፍላጎት አስቀድመው ሂደቱን ሲያጣጥሉ እንደነበር ጠቁሟል።
ኢዜማ በስተመጨረሻም፣ ያሉትን ውስብስብ ችግሮች ተጋፍጦ የተሻለ ስኬት ማስመዝገቡን ጠቅሶ፣ ሥልጣን መያዝ የሚቻለው በሰላማዊ መንገድ ብቻ በመሆኑ በቀጣይም ለዲሞክራሲ ግንባታ በቁርጠኝነት እንደሚሠራ አስታውቋል።
Seledadotio
Seledadotio
2 months ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) ታዋቂዋ ኢትዮጵያዊት አርቲስት መሰረት መብራቴ፣ በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ አርሲ ዞን በኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነት ተከታዮች ላይ እየደረሰ ያለውን ተደጋጋሚ ጥቃት፣ መፈናቀል እና ግድያ በተመለከተ መንግሥትን እና የፍትሕ አካላትን ክፉኛ የሚወቅስ ጠንካራ መልእክት አስተላለፈች። አርቲስቷ በማኅበራዊ ትስስር ገጿ ባጋራችው እና በማህበራዊ ትሥሥር ላይ በግልጽ በሚታየው ጽሁፍ፣ የዜጎችን ደህንነት ማስጠበቅ ያልቻለውን ሥርዓት እና የሕግ ማስከበር ክፍተቱን በጽኑ ተችታለች።
በመልእክቷም "የኦርቶዶክሳውያን ሞትና መከራ እስከመቼ?!" በማለት መሠረታዊ የፍትሕ ጥያቄ ያነሳች ሲሆን፣ ምስራቅ አርሲን "የደም ምድር" ስትል ገልጻዋለች። ድርጊቱ ማቆሚያ የሌለው እልቂት እና ሰሚ የሌለው ጩኸት መሆኑን የጠቀሰችው አርቲስቷ የንጹሃን ደም ፍትሕ እየጠየቀ መሆኑን በአጽንኦት አስገንዝባለች። በተለይም በመልእክቷ ላይ "ከምድራዊ ዳኛ ፍትህ ባናገኝ፣ የሰማዩ አምላክ ይፈርዳችኋል!!!" በማለት ያሰፈረችው ሐሳብ የሕግ የበላይነት መጓደልን እና ምድራዊ የፍትሕ ተቋማት የዜጎችን ደህንነት በማስጠበቅ ረገድ ያሳዩትን ደካማ አፈጻጸም በቀጥታ የሚሞግት ወሳኝ መልእክት ነው።
በቅርብ ዓመታት በኢትዮጵያ የተለያዩ አካባቢዎች በተለይም በምስራቅ አርሲ እና አካባቢው ማንነትን እና ሃይማኖትን መሠረት ያደረጉ ጥቃቶች መበራከታቸውን የሰብአዊ መብት ተሟጋቾች፣ የሃይማኖት ተቋማት እና እንደ ኢዜማ፣ እናት ፓርቲ ያሉ የፖለቲካ ፓርቲዎች በተደጋጋሚ ሲገልጹ ቆይተዋል። በእነዚህ ክስተቶች የተነሳ በርካታ ዜጎች ሕይወታቸውን ያጡ ሲሆን፣ አያሌዎች ደግሞ ከቀያቸው ተፈናቅለው ለከፍተኛ እንግልት ተዳርገዋል።
በዚህ አውድ ውስጥ የሀገሪቱ ታዋቂ ግለሰቦች እና የኪነ-ጥበብ ሰዎች ከዝምታ ወጥተው ድምፃቸውን ማሰማት መጀመራቸው ትልቅ ትርጉም አለው። እንደ መሰረት መብራቴ ያሉ ተጽዕኖ ፈጣሪ ሰዎች እንዲህ ያሉ የአደባባይ ጩኸቶችን ማሰማታቸው፣ ችግሩ ብሔራዊ ትኩረት እንዲያገኝ ከማድረጉም ባለፈ የፍትሕ ተቋማት እና የጸጥታ ኃይሎች በዜጎች ላይ እየደረሰ ያለውን ጥቃት በአፋጣኝ አምነው ተገቢውን እርምጃ እንዲወስዱ ከፍተኛ ማኅበራዊ ጫና ይፈጥራል።
አርቲስት መሰረት መብራቴ "ወገኖቼ ነፍሳችሁን በቅዱሳን እቅፍ ይቀበለው" በማለት በግፉ ሕይወታቸውን ላጡ ንጹሃን ዜጎች ያላትን ጥልቅ ሀዘን በመግለጽ መልእክቷን አጠቃላለች።
በመልእክቷም "የኦርቶዶክሳውያን ሞትና መከራ እስከመቼ?!" በማለት መሠረታዊ የፍትሕ ጥያቄ ያነሳች ሲሆን፣ ምስራቅ አርሲን "የደም ምድር" ስትል ገልጻዋለች። ድርጊቱ ማቆሚያ የሌለው እልቂት እና ሰሚ የሌለው ጩኸት መሆኑን የጠቀሰችው አርቲስቷ የንጹሃን ደም ፍትሕ እየጠየቀ መሆኑን በአጽንኦት አስገንዝባለች። በተለይም በመልእክቷ ላይ "ከምድራዊ ዳኛ ፍትህ ባናገኝ፣ የሰማዩ አምላክ ይፈርዳችኋል!!!" በማለት ያሰፈረችው ሐሳብ የሕግ የበላይነት መጓደልን እና ምድራዊ የፍትሕ ተቋማት የዜጎችን ደህንነት በማስጠበቅ ረገድ ያሳዩትን ደካማ አፈጻጸም በቀጥታ የሚሞግት ወሳኝ መልእክት ነው።
በቅርብ ዓመታት በኢትዮጵያ የተለያዩ አካባቢዎች በተለይም በምስራቅ አርሲ እና አካባቢው ማንነትን እና ሃይማኖትን መሠረት ያደረጉ ጥቃቶች መበራከታቸውን የሰብአዊ መብት ተሟጋቾች፣ የሃይማኖት ተቋማት እና እንደ ኢዜማ፣ እናት ፓርቲ ያሉ የፖለቲካ ፓርቲዎች በተደጋጋሚ ሲገልጹ ቆይተዋል። በእነዚህ ክስተቶች የተነሳ በርካታ ዜጎች ሕይወታቸውን ያጡ ሲሆን፣ አያሌዎች ደግሞ ከቀያቸው ተፈናቅለው ለከፍተኛ እንግልት ተዳርገዋል።
በዚህ አውድ ውስጥ የሀገሪቱ ታዋቂ ግለሰቦች እና የኪነ-ጥበብ ሰዎች ከዝምታ ወጥተው ድምፃቸውን ማሰማት መጀመራቸው ትልቅ ትርጉም አለው። እንደ መሰረት መብራቴ ያሉ ተጽዕኖ ፈጣሪ ሰዎች እንዲህ ያሉ የአደባባይ ጩኸቶችን ማሰማታቸው፣ ችግሩ ብሔራዊ ትኩረት እንዲያገኝ ከማድረጉም ባለፈ የፍትሕ ተቋማት እና የጸጥታ ኃይሎች በዜጎች ላይ እየደረሰ ያለውን ጥቃት በአፋጣኝ አምነው ተገቢውን እርምጃ እንዲወስዱ ከፍተኛ ማኅበራዊ ጫና ይፈጥራል።
አርቲስት መሰረት መብራቴ "ወገኖቼ ነፍሳችሁን በቅዱሳን እቅፍ ይቀበለው" በማለት በግፉ ሕይወታቸውን ላጡ ንጹሃን ዜጎች ያላትን ጥልቅ ሀዘን በመግለጽ መልእክቷን አጠቃላለች።
2 months ago
ኢዜማን ምረጥ ያለው ኢህአዴግ በእስራት ተቀጣ...
በደቡብ አሪ ወረዳ፣ ገድር ቀበሌ በምርጫ ዕለት የተከለከለ የፖለቲካ ቅስቀሳ በማድረጉ የተከሰሰው አቶ ኢህአዴግ ኃይሉ የ6 ወር ቀላል እስራት ተፈረደበት።
የዐቃቤ ህግ ክስ እንደሚያስረዳው፣ ተከሳሹ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. ምርጫ ጣቢያ አቅራቢያ ድምፅ ለመስጠት ወደ ጣቢያው ይሄድ የነበረን ወጣት ለኢዜማ ድምፅ እንዲሰጥ በመገፋፋት በምርጫ ሥነ-ምግባር አዋጅ ቁጥር 1162/2011 የተደነገገውን ክልከላ ጥሷል።
ጉዳዩን ሲመለከት የቆየው የደቡብ አሪ ወረዳ ፍርድ ቤት፣ የዐቃቤ ህግን የሰው ምስክሮች እና የተከሳሹን የእምነት ክህደት ቃል ካዳመጠ በኋላ ተከሳሹ መከላከያ ማስረጃ ማቅረብ ባለመቻሉ ጥፋተኛ ብሎታል። ፍርድ ቤቱ ተከሳሹ የሦስት ልጆች አሳዳጊ መሆኑን እንደ ማቅለያ በመቀበል፣ በቀጣይ ለሌሎችም ማስጠንቀቂያ ይሆን ዘንድ በ6 ወር ቀላል እስራት እንዲቀጣ ውሳኔ አሳልፏል። ፍርዱ ለሁለት ዓመት በግልጽ ገደብ እንዲፈጸም ታዟል።
Seledadotio
Seledadotio
በደቡብ አሪ ወረዳ፣ ገድር ቀበሌ በምርጫ ዕለት የተከለከለ የፖለቲካ ቅስቀሳ በማድረጉ የተከሰሰው አቶ ኢህአዴግ ኃይሉ የ6 ወር ቀላል እስራት ተፈረደበት።
የዐቃቤ ህግ ክስ እንደሚያስረዳው፣ ተከሳሹ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. ምርጫ ጣቢያ አቅራቢያ ድምፅ ለመስጠት ወደ ጣቢያው ይሄድ የነበረን ወጣት ለኢዜማ ድምፅ እንዲሰጥ በመገፋፋት በምርጫ ሥነ-ምግባር አዋጅ ቁጥር 1162/2011 የተደነገገውን ክልከላ ጥሷል።
ጉዳዩን ሲመለከት የቆየው የደቡብ አሪ ወረዳ ፍርድ ቤት፣ የዐቃቤ ህግን የሰው ምስክሮች እና የተከሳሹን የእምነት ክህደት ቃል ካዳመጠ በኋላ ተከሳሹ መከላከያ ማስረጃ ማቅረብ ባለመቻሉ ጥፋተኛ ብሎታል። ፍርድ ቤቱ ተከሳሹ የሦስት ልጆች አሳዳጊ መሆኑን እንደ ማቅለያ በመቀበል፣ በቀጣይ ለሌሎችም ማስጠንቀቂያ ይሆን ዘንድ በ6 ወር ቀላል እስራት እንዲቀጣ ውሳኔ አሳልፏል። ፍርዱ ለሁለት ዓመት በግልጽ ገደብ እንዲፈጸም ታዟል።
Seledadotio
Seledadotio
2 months ago
ኢዜማን ምረጥ ያለው ኢህአዴግ በእስራት ተቀጣ
#fastmereja I በደቡብ አሪ ወረዳ፣ ገድር ቀበሌ በምርጫ ዕለት የተከለከለ የፖለቲካ ቅስቀሳ በማድረጉ የተከሰሰው አቶ ኢህአዴግ ኃይሉ የ6 ወር ቀላል እስራት ተፈረደበት።
የዐቃቤ ህግ ክስ እንደሚያስረዳው፣ ተከሳሹ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. ምርጫ ጣቢያ አቅራቢያ ድምፅ ለመስጠት ወደ ጣቢያው ይሄድ የነበረን ወጣት ለኢዜማ ድምፅ እንዲሰጥ በመገፋፋት በምርጫ ሥነ-ምግባር አዋጅ ቁጥር 1162/2011 የተደነገገውን ክልከላ ጥሷል።
ጉዳዩን ሲመለከት የቆየው የደቡብ አሪ ወረዳ ፍርድ ቤት፣ የዐቃቤ ህግን የሰው ምስክሮች እና የተከሳሹን የእምነት ክህደት ቃል ካዳመጠ በኋላ ተከሳሹ መከላከያ ማስረጃ ማቅረብ ባለመቻሉ ጥፋተኛ ብሎታል። ፍርድ ቤቱ ተከሳሹ የሦስት ልጆች አሳዳጊ መሆኑን እንደ ማቅለያ በመቀበል፣ በቀጣይ ለሌሎችም ማስጠንቀቂያ ይሆን ዘንድ በ6 ወር ቀላል እስራት እንዲቀጣ ውሳኔ አሳልፏል። ፍርዱ ለሁለት ዓመት በግልጽ ገደብ እንዲፈጸም ታዟል።
#fastmereja I በደቡብ አሪ ወረዳ፣ ገድር ቀበሌ በምርጫ ዕለት የተከለከለ የፖለቲካ ቅስቀሳ በማድረጉ የተከሰሰው አቶ ኢህአዴግ ኃይሉ የ6 ወር ቀላል እስራት ተፈረደበት።
የዐቃቤ ህግ ክስ እንደሚያስረዳው፣ ተከሳሹ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. ምርጫ ጣቢያ አቅራቢያ ድምፅ ለመስጠት ወደ ጣቢያው ይሄድ የነበረን ወጣት ለኢዜማ ድምፅ እንዲሰጥ በመገፋፋት በምርጫ ሥነ-ምግባር አዋጅ ቁጥር 1162/2011 የተደነገገውን ክልከላ ጥሷል።
ጉዳዩን ሲመለከት የቆየው የደቡብ አሪ ወረዳ ፍርድ ቤት፣ የዐቃቤ ህግን የሰው ምስክሮች እና የተከሳሹን የእምነት ክህደት ቃል ካዳመጠ በኋላ ተከሳሹ መከላከያ ማስረጃ ማቅረብ ባለመቻሉ ጥፋተኛ ብሎታል። ፍርድ ቤቱ ተከሳሹ የሦስት ልጆች አሳዳጊ መሆኑን እንደ ማቅለያ በመቀበል፣ በቀጣይ ለሌሎችም ማስጠንቀቂያ ይሆን ዘንድ በ6 ወር ቀላል እስራት እንዲቀጣ ውሳኔ አሳልፏል። ፍርዱ ለሁለት ዓመት በግልጽ ገደብ እንዲፈጸም ታዟል።
2 months ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) ‹‹አለም አቀፍ ሚዲያዎች በምርጫው ዙሪያ ያልተመጣጠነ አሉታዊ ትረካ እያቀረቡ ነው›› ሲሉ የኢዜማ መሪ ገለፁ፡፡ የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ ፓርቲ መሪ የሆኑት አቶ እዮብ መሳፍንት አለም አቀፍ ሚዲያዎች ከምርጫው በፊት ያልተመጣጠነ አሉታዊ ትርክት እያቀረቡ መሆኑን በመግለፅ ወቀሱ፡፡
እኚህ የተቃዋሚ ፓርቲ መሪ ሚዲያዎቹ ‹‹የአገር ውስጥ እድገትንና የመራጮችን ተስፋ ችላ በማለት በአሉታዊ ዘገባዎች ላይ ተጠምደዋል›› በማለትም ገልፀዋል፡፡ አቶ እዮብ ከራይዝ ኤንድ ሻይን ጋር ባደረጉት ቃለምልልስ ምርጫው በግጭት የተሸፈነ፣ አነስተኛ ተሳትፎ ያለበትና ተአማኒነት እንደሚያንሰው በስፋት በአለም አቀፍ ሚዲያዎች የተዘገበውን አጣጥለውታል፡፡
በአንዳንድ አካባቢዎች በተለይም በትግራይ ክልልና በአማራ ክልል ውስጥ ባለው አለመረጋጋት ምርጫ አለመካሄዱን ያረጋገጡት መሪው ይሁንና እነዚህ አካባቢዎች ከአጠቃላይ ምርጫው የተወሰነ ክፍል እንደሚሸፍኑ ገልፀዋል፡፡ በአብዛኛው የአገሪቱ ክፍል ምርጫው በመካሄዱ የምርጫው ውጤት በመንግስት ምስረታ ላይ ተፅእኖ እንደማይፈጥር መናገራቸውን ቻናል አፍሪካ ካቀረበው ዘገባ ተመልክተናል፡፡
እኚህ የተቃዋሚ ፓርቲ መሪ ሚዲያዎቹ ‹‹የአገር ውስጥ እድገትንና የመራጮችን ተስፋ ችላ በማለት በአሉታዊ ዘገባዎች ላይ ተጠምደዋል›› በማለትም ገልፀዋል፡፡ አቶ እዮብ ከራይዝ ኤንድ ሻይን ጋር ባደረጉት ቃለምልልስ ምርጫው በግጭት የተሸፈነ፣ አነስተኛ ተሳትፎ ያለበትና ተአማኒነት እንደሚያንሰው በስፋት በአለም አቀፍ ሚዲያዎች የተዘገበውን አጣጥለውታል፡፡
በአንዳንድ አካባቢዎች በተለይም በትግራይ ክልልና በአማራ ክልል ውስጥ ባለው አለመረጋጋት ምርጫ አለመካሄዱን ያረጋገጡት መሪው ይሁንና እነዚህ አካባቢዎች ከአጠቃላይ ምርጫው የተወሰነ ክፍል እንደሚሸፍኑ ገልፀዋል፡፡ በአብዛኛው የአገሪቱ ክፍል ምርጫው በመካሄዱ የምርጫው ውጤት በመንግስት ምስረታ ላይ ተፅእኖ እንደማይፈጥር መናገራቸውን ቻናል አፍሪካ ካቀረበው ዘገባ ተመልክተናል፡፡
Sponsored by
Surafel
2 months ago
"እስከሁን በመላ ሀገሪቱ ባለው የምርጫ ሂደት ችግር እንዳላጋጠመ አረጋግጠናል" የኢዜማ መሪ
የኢዜማ ፓርቲ መሪ እዮብ መሳፍንት በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ 9 የምርጫ ጣቢያ ተገኝተው ድምጽ ሰጥተዋል። የኢዜማው መሪ እስከአሁን የምርጫ ሂደቱ መልካም መኾኑን ገልጸው የሚያጋጥሙ ችግሮችን ለመፍታት ማዕከላዊ የፓርቲ ቢሮ ማዘጋጀታቸውንም ገልጸዋል። እስከሁን በመላ ሀገሪቱ ባለው የምርጫ ሂደት ችግር እንዳላጋጠመ በሪፖርት አረጋግጠናልም ብለዋል።
Seledadotio
Seledadotio
የኢዜማ ፓርቲ መሪ እዮብ መሳፍንት በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ 9 የምርጫ ጣቢያ ተገኝተው ድምጽ ሰጥተዋል። የኢዜማው መሪ እስከአሁን የምርጫ ሂደቱ መልካም መኾኑን ገልጸው የሚያጋጥሙ ችግሮችን ለመፍታት ማዕከላዊ የፓርቲ ቢሮ ማዘጋጀታቸውንም ገልጸዋል። እስከሁን በመላ ሀገሪቱ ባለው የምርጫ ሂደት ችግር እንዳላጋጠመ በሪፖርት አረጋግጠናልም ብለዋል።
Seledadotio
Seledadotio
2 months ago
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በኦሮሚያ ክልል በምትገኘው በሻሻ ዛሬ ጠዋት ለሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ድምጽ ሰጥተዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በኦሮሚያ ክልል ጅማ ዞን ውስጥ በሚገኘው ጎማ 2 የምርጫ ክልል ከሁለት የተቃዋሚ ፖለቲካ ፓርቲ ዕጩዎች ጋር ይወዳደራሉ።
ነፃነትና እኩልነት ፓርቲን የሚወክሉት ዳግም ዋሪሶ እና የኢዜማ ዕጩ ካልድ ጃማል ሀይደር
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በኦሮሚያ ክልል ጅማ ዞን ውስጥ በሚገኘው ጎማ 2 የምርጫ ክልል ከሁለት የተቃዋሚ ፖለቲካ ፓርቲ ዕጩዎች ጋር ይወዳደራሉ።
ነፃነትና እኩልነት ፓርቲን የሚወክሉት ዳግም ዋሪሶ እና የኢዜማ ዕጩ ካልድ ጃማል ሀይደር
Comments