የኢዜማ የድጋፍ መግለጫ
***
ለሰላም የቀረበውን ጥሪ አስመልክቶ ከኢዜማ የተሠጠ የድጋፍ መግለጫ!!
በ 8 ፓርቲዎችና 11 ሲቪክ ማሕበራት የተቋቋመው የትግራይ ሰላምና ለውጥ ፈላጊዎች እንቅስቃሴ ሕጋዊ አካልነቱን ባጣው ሕወሓት አማካኝነት በትግራይ ህዝብ ላይ እየተደረገ ያለው አፈና፣ ስቃይ እና እንግልት እንዲቆም እና ጦርነት እንዲቀር ጫና ለማድረግ ያለመ የሰላማዊ ሰልፍ በአዲስ አበባ እንደጠራ መረጃ ደርሶናል፤ የለውጥ እንቅስቃሴው ሁሉም ይህን ሰላማዊ ዓላማ የሚደግፉ ኢትዮጵያውያን በሰልፉ ድጋፋቸውን እንዲሰጡም ጥሪ አቅርቧል።
ፓርቲያችን ኢዜማ የትግራይን ህዝብ ከዳግም ጦርነት እና ስቃይ ለማዳን የሚደረጉ ሰላማዊ እንቅስቃሴዎች ሁሉ እንደሚደግፍ በተደጋጋሚ በገለፀው መሠረት ለዚህ ሰላማዊ ሰልፍ ይፋዊ ድጋፉን እየገለፀ የኢዜማ አባላትና ደጋፊዎችም በሰልፉ በመገኘት እምቢ ለጦርነት የሚል ድጋፋቸውን እንዲያሳዩ ጥሪውን ያቀርባል።
እምቢ ለጦርነት!
የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ (ኢዜማ)
***
ለሰላም የቀረበውን ጥሪ አስመልክቶ ከኢዜማ የተሠጠ የድጋፍ መግለጫ!!
በ 8 ፓርቲዎችና 11 ሲቪክ ማሕበራት የተቋቋመው የትግራይ ሰላምና ለውጥ ፈላጊዎች እንቅስቃሴ ሕጋዊ አካልነቱን ባጣው ሕወሓት አማካኝነት በትግራይ ህዝብ ላይ እየተደረገ ያለው አፈና፣ ስቃይ እና እንግልት እንዲቆም እና ጦርነት እንዲቀር ጫና ለማድረግ ያለመ የሰላማዊ ሰልፍ በአዲስ አበባ እንደጠራ መረጃ ደርሶናል፤ የለውጥ እንቅስቃሴው ሁሉም ይህን ሰላማዊ ዓላማ የሚደግፉ ኢትዮጵያውያን በሰልፉ ድጋፋቸውን እንዲሰጡም ጥሪ አቅርቧል።
ፓርቲያችን ኢዜማ የትግራይን ህዝብ ከዳግም ጦርነት እና ስቃይ ለማዳን የሚደረጉ ሰላማዊ እንቅስቃሴዎች ሁሉ እንደሚደግፍ በተደጋጋሚ በገለፀው መሠረት ለዚህ ሰላማዊ ሰልፍ ይፋዊ ድጋፉን እየገለፀ የኢዜማ አባላትና ደጋፊዎችም በሰልፉ በመገኘት እምቢ ለጦርነት የሚል ድጋፋቸውን እንዲያሳዩ ጥሪውን ያቀርባል።
እምቢ ለጦርነት!
የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ (ኢዜማ)
22 days ago