3 hours ago
በሸገር ከተማ ለ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና…
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 7፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የሸገር ከተማ አስተዳደር ለ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና አስፈላጊውን ዝግጅት አድርጊያለሁ አለ።
የከተማዋ ትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ ፊራኪያ ካሳሁን ለፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን እንደገለጹት÷ ዘንድሮው 8 ሺህ 932 ተማሪዎች በከተማ አስተዳደሩ የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ይወስዳሉ።
በከተማ አስተዳደሩ ለፈተናው ድጋፍ ከማድረግ ጀምሮ ግብዓቶችን በማሟላት ተማሪዎች የተሻለ ውጤት እንዲያስመዘግቡ አስፈላጊ ዝግጅት መደረጉን አመላክተዋል።
የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ ጠንካራ የድጋፍ እና የክትትል ሥርዓት መዘርጋቱን ጠቅሰው÷ በዚህም በከተማዋ የትምህርት ተቋማትን ማስፋፋት፣ የተማሪዎችን ተሳትፎ ማጠናከርና ትምህርት ቤቶች የመገንባት ስራዎች መከናወናቸውን ተናግረዋል።
እንዲሁም የመምህራንን አቅም ማጠናከር እና የመማሪያ መሳሪያዎችን በማሟላት ለመማር ማስተማር ስራ ትኩረት መሰጠቱን ገልጸዋል።
በትምህርት ጥራት ላይ ያሉ ክፍተቶችን በመለየትና በመቅረፍ የተማሪዎችን ውጤት ለማሻሻል በተጠናከረ መንገድ መሰራቱንም አመልክተዋል።
በታሪክ አዱኛ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 7፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የሸገር ከተማ አስተዳደር ለ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና አስፈላጊውን ዝግጅት አድርጊያለሁ አለ።
የከተማዋ ትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ ፊራኪያ ካሳሁን ለፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን እንደገለጹት÷ ዘንድሮው 8 ሺህ 932 ተማሪዎች በከተማ አስተዳደሩ የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ይወስዳሉ።
በከተማ አስተዳደሩ ለፈተናው ድጋፍ ከማድረግ ጀምሮ ግብዓቶችን በማሟላት ተማሪዎች የተሻለ ውጤት እንዲያስመዘግቡ አስፈላጊ ዝግጅት መደረጉን አመላክተዋል።
የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ ጠንካራ የድጋፍ እና የክትትል ሥርዓት መዘርጋቱን ጠቅሰው÷ በዚህም በከተማዋ የትምህርት ተቋማትን ማስፋፋት፣ የተማሪዎችን ተሳትፎ ማጠናከርና ትምህርት ቤቶች የመገንባት ስራዎች መከናወናቸውን ተናግረዋል።
እንዲሁም የመምህራንን አቅም ማጠናከር እና የመማሪያ መሳሪያዎችን በማሟላት ለመማር ማስተማር ስራ ትኩረት መሰጠቱን ገልጸዋል።
በትምህርት ጥራት ላይ ያሉ ክፍተቶችን በመለየትና በመቅረፍ የተማሪዎችን ውጤት ለማሻሻል በተጠናከረ መንገድ መሰራቱንም አመልክተዋል።
በታሪክ አዱኛ
3 hours ago
በንጽህና መጠበቂያ ምርቶች ላይ የታለመው የዋጋ ቅናሽ በተግባር ባለመዋሉ መንግስት ጥብቅ የገበያ ቁጥጥር እንዲያደርግ ተጠየቀ
የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች እና የልማት አጋሮች በሴቶች የወር አበባ ንጽህና መጠበቂያ ምርቶች ላይ የታለመው የችርቻሮ ዋጋ ቅናሽ ለተጠቃሚዎች በትክክል ተፈጻሚ ባለመሆኑ፣ የኢትዮጵያ መንግስት ጥብቅ የገበያ ቁጥጥር እና የተጠያቂነት አሰራር እንዲዘረጋ አሳሰቡ።
መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች እንደሚሉት፤ በሴቶች ላይ የሚደርሰውን የኢኮኖሚ ጫና ለመቀነስ ቀደም ሲል የፊስካል ማሻሻያ እርምጃዎች ቢወሰዱም፣ መዋቅራዊ መሰናክሎች፣ ደካማ የአቅርቦት ሰንሰለት ቁጥጥር እና ዝቅተኛ ግንዛቤ ሂደቱን በማስተጓጎላቸው በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሴቶች እና ልጃገረዶች አሁንም ለችግር ተጋልጠዋል።
የኤች.አይ.ቪ ጤና ጥበቃ ፈንድ (AHF) ኢትዮጵያ የቅድመ መከላከል፣ የአፍሪካ ህብረት ግንኙነት እና የዕድገት ድጋፍ ስራ አስኪያጅ አቶ ቶለሳ ኦላና ጉዳዩን በተመለከተ ለካፒታል ጋዜጣ እንደገለጹት፤ የወር አበባ ጤና መጠበቂያ ምርቶች እጥረት እና ያለመገኘት በኢትዮጵያ የፆታ እኩልነት፣ ጤና፣ ትምህርት እና የኢኮኖሚ ምርታማነት ላይ ትልቅ እንቅፋት እየሆነ መጥቷል።
በ 2017 የቀረበው እና በምርቶቹ ላይ የሚስተዋሉ መዋቅራዊ መሰናክሎችን ለማስወገድ በተዘጋጀው ረቂቅ የፖሊሲ ሰነድ ላይ ይህ ጉዳይ በስፋት ተዳሷል።
በጤና ሚኒስቴር፣ በትምህርት ሚኒስቴር እና ከ10 በላይ አጋር ድርጅቶች (AHF፣ ዩኒሴፍ እና ሌሎችም ጨምሮ) እንዲሁም በአገር ውስጥ በድጋሚ ጥቅም ላይ የሚውሉ ሞዴሶችን ከሚያመርቱ ድርጅቶች ጋር በጋራ የተዘጋጀው ይህ ረቂቅ ሰነድ እንደሚያሳየው፤ በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ ዘመናዊ የወር አበባ ንጽህና መጠበቂያ ምርቶችን ማግኘት የሚችሉት 30 በመቶ ያህሉ ሴቶች ብቻ ናቸው።
የዚህ እጥረት መዘዝ ከባድ መሆኑን የገለጹት አቶ ቶለሳ፣ ከ10 ታዳጊ ልጃገረዶች መካከል አንዷ በወር አበባ ምክንያት መደበኛ የትምህርት ቀናት የምታጣ ሲሆን፣ ብዙ ሴቶች ደግሞ በስራ ቦታቸው ላይ ምርታማነታቸው እንዲቀንስ ወይም ከስራ ለመቅረት ተገድደዋል ብለዋል።
ምንም እንኳን መንግስት ቀደም ሲል የማስመጫ ታሪፎችን ቢያስተካክልም፣ ሊጣሉ በሚችሉ ሞዴሶች እና ሌሎች ምርቶች ላይ አሁንም 15 በመቶ ከፍተኛ የተጨማሪ እሴት ታክስ ይተገበራል። ችግሩ ይበልጥ የተወሳሰበው በተጠናቀቁ ምርቶች ላይ በሚጣለው 10 በመቶ የጉምሩክ ቀረጥ እና ለማምረቻነት በሚያገለግሉ ጥሬ ዕቃዎች ላይ በሚጣለው ከፍተኛ ታክስ ምክንያት ነው።
አቶ ቶለሳ ኦላና እንዳሉት፤ ከአስመጪዎች፣ ከችርቻሮ ነጋዴዎች እና ከማህበራዊ ማሻሻጫ አካላት ጋር ከፍተኛ የፖሊሲ ውይይቶች ቢደረጉም፣ በህብረተሰቡ ደረጃ የታየ ተጨባጭ ለውጥ የለም። ከአምራቾች፣ አስመጪዎች፣ አከፋፋዮች እና የማህበራዊ ማሻሻጫ መረቦች ጋር ሰፊ ውይይት ቢደረግም ስለ ታክስ ነፃ መብቶች ያለው ግንዛቤ አሁንም ዝቅተኛ መሆኑን ጠቁመዋል።
Via capital
የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች እና የልማት አጋሮች በሴቶች የወር አበባ ንጽህና መጠበቂያ ምርቶች ላይ የታለመው የችርቻሮ ዋጋ ቅናሽ ለተጠቃሚዎች በትክክል ተፈጻሚ ባለመሆኑ፣ የኢትዮጵያ መንግስት ጥብቅ የገበያ ቁጥጥር እና የተጠያቂነት አሰራር እንዲዘረጋ አሳሰቡ።
መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች እንደሚሉት፤ በሴቶች ላይ የሚደርሰውን የኢኮኖሚ ጫና ለመቀነስ ቀደም ሲል የፊስካል ማሻሻያ እርምጃዎች ቢወሰዱም፣ መዋቅራዊ መሰናክሎች፣ ደካማ የአቅርቦት ሰንሰለት ቁጥጥር እና ዝቅተኛ ግንዛቤ ሂደቱን በማስተጓጎላቸው በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሴቶች እና ልጃገረዶች አሁንም ለችግር ተጋልጠዋል።
የኤች.አይ.ቪ ጤና ጥበቃ ፈንድ (AHF) ኢትዮጵያ የቅድመ መከላከል፣ የአፍሪካ ህብረት ግንኙነት እና የዕድገት ድጋፍ ስራ አስኪያጅ አቶ ቶለሳ ኦላና ጉዳዩን በተመለከተ ለካፒታል ጋዜጣ እንደገለጹት፤ የወር አበባ ጤና መጠበቂያ ምርቶች እጥረት እና ያለመገኘት በኢትዮጵያ የፆታ እኩልነት፣ ጤና፣ ትምህርት እና የኢኮኖሚ ምርታማነት ላይ ትልቅ እንቅፋት እየሆነ መጥቷል።
በ 2017 የቀረበው እና በምርቶቹ ላይ የሚስተዋሉ መዋቅራዊ መሰናክሎችን ለማስወገድ በተዘጋጀው ረቂቅ የፖሊሲ ሰነድ ላይ ይህ ጉዳይ በስፋት ተዳሷል።
በጤና ሚኒስቴር፣ በትምህርት ሚኒስቴር እና ከ10 በላይ አጋር ድርጅቶች (AHF፣ ዩኒሴፍ እና ሌሎችም ጨምሮ) እንዲሁም በአገር ውስጥ በድጋሚ ጥቅም ላይ የሚውሉ ሞዴሶችን ከሚያመርቱ ድርጅቶች ጋር በጋራ የተዘጋጀው ይህ ረቂቅ ሰነድ እንደሚያሳየው፤ በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ ዘመናዊ የወር አበባ ንጽህና መጠበቂያ ምርቶችን ማግኘት የሚችሉት 30 በመቶ ያህሉ ሴቶች ብቻ ናቸው።
የዚህ እጥረት መዘዝ ከባድ መሆኑን የገለጹት አቶ ቶለሳ፣ ከ10 ታዳጊ ልጃገረዶች መካከል አንዷ በወር አበባ ምክንያት መደበኛ የትምህርት ቀናት የምታጣ ሲሆን፣ ብዙ ሴቶች ደግሞ በስራ ቦታቸው ላይ ምርታማነታቸው እንዲቀንስ ወይም ከስራ ለመቅረት ተገድደዋል ብለዋል።
ምንም እንኳን መንግስት ቀደም ሲል የማስመጫ ታሪፎችን ቢያስተካክልም፣ ሊጣሉ በሚችሉ ሞዴሶች እና ሌሎች ምርቶች ላይ አሁንም 15 በመቶ ከፍተኛ የተጨማሪ እሴት ታክስ ይተገበራል። ችግሩ ይበልጥ የተወሳሰበው በተጠናቀቁ ምርቶች ላይ በሚጣለው 10 በመቶ የጉምሩክ ቀረጥ እና ለማምረቻነት በሚያገለግሉ ጥሬ ዕቃዎች ላይ በሚጣለው ከፍተኛ ታክስ ምክንያት ነው።
አቶ ቶለሳ ኦላና እንዳሉት፤ ከአስመጪዎች፣ ከችርቻሮ ነጋዴዎች እና ከማህበራዊ ማሻሻጫ አካላት ጋር ከፍተኛ የፖሊሲ ውይይቶች ቢደረጉም፣ በህብረተሰቡ ደረጃ የታየ ተጨባጭ ለውጥ የለም። ከአምራቾች፣ አስመጪዎች፣ አከፋፋዮች እና የማህበራዊ ማሻሻጫ መረቦች ጋር ሰፊ ውይይት ቢደረግም ስለ ታክስ ነፃ መብቶች ያለው ግንዛቤ አሁንም ዝቅተኛ መሆኑን ጠቁመዋል።
Via capital
5 hours ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የኢትዮጵያ ባህር ትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ አገልግሎት ድርጅት (ESL) ከ40 ዓመታት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ የሀገሪቱን የነዳጅ እና የፔትሮሊየም ምርቶች የማጓጓዝ ስራ በይፋ መጀመሩን ዛሬ በአዲስ አበባ ታትሞ የወጣው ካፒታል እንግሊዘኛው ጋዜጣ ዘግቧል። ይህ ታሪካዊ ጅምር ኢትዮጵያ ከሱዳን ነዳጅ ማስገባት ካቆመች በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ከአፍሪካ (ከአህጉሪቱ) ሀገር ነዳጅ ያገኘችበትንም አዲስ ምዕራፍ ከፍቷል።
በአሜሪካ በእስራኤል እና በኢራን መካከል በተፈጠረው ግጭት ምክንያት በዓለም አቀፉ የነዳጅ መተላለፊያ ላይ የተፈጠረውን መስተጓጎል ተከትሎ፣ የኢትዮጵያ መንግስት የነዳጅ ግዥ ስትራቴጂውን ወደ ምዕራብ እስያ እና ናይጄሪያ በማስፋት አማራጮችን ፈጥሯል። በዚህም መሰረት፣ በቢሊየነሩ አሊኮ ዳንጎቴ ከሚተዳደረው የናይጄሪያው 'ዳንጎቴ ፔትሮሊየም ሪፋይነሪ' 120,000 ሜትሪክ ቶን የአቪዬሽን (የአውሮፕላን) እና የናፍጣ ነዳጅ በተሳካ ሁኔታ በ3 መርከቦች ወደ ጅቡቲ ሆራይዘን ተርሚናል ተጓጉዟል። ከዚህ ውስጥ 80,000 ሜትሪክ ቶኑ የአውሮፕላን ነዳጅ ነው።
ባለፉት አራት አስርት ዓመታት የነዳጅ ማጓጓዝ ስራውን በብቸኝነት ሲያከናውን የቆየው የኢትዮጵያ የነዳጅ አቅራቢ ድርጅት (EPSE) ሲሆን፣ አሁን ግን መንግስት ዘርፉን ክፍት በማድረግ የግል ባለሀብቶች፣ ዓለም አቀፍ ድርጅቶች እና የዲፕሎማቲክ ማህበረሰቡ በራሳቸው የውጭ ምንዛሬ ነዳጅ ማስገባት የሚችሉበትን መመሪያ አውጥቷል።
ኢትዮጵያ ነዳጅ የማታመርት በመሆኗ የገቢ ንግድ በጀቷን ሩብ ያህል ለነዳጅ የምታውል ሲሆን፣ በመጪው በጀት ዓመት የነዳጅ ወጪዋ እስከ 6 ቢሊዮን ዶላር ሊደርስ እንደሚችል የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ ለፓርላማው መግለጻቸውን በዘ-ሐበሻ ዜና መዘገባችን ይታወሳል። መንግስት በያዘው የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ መሰረት፣ የነዳጅ ድጎማን ቀስ በቀስ ለመቀነስ በማቀድ በመጪው በጀት ዓመት ለዘርፉ 20 ቢሊዮን ብር ብቻ የድጎማ በጀት አቅርቧል፤ ይህም ካለፈው ዓመት ጋር ሲነጻጸር ከፍተኛ ቅናሽ ያሳየ ነው።
በአሜሪካ በእስራኤል እና በኢራን መካከል በተፈጠረው ግጭት ምክንያት በዓለም አቀፉ የነዳጅ መተላለፊያ ላይ የተፈጠረውን መስተጓጎል ተከትሎ፣ የኢትዮጵያ መንግስት የነዳጅ ግዥ ስትራቴጂውን ወደ ምዕራብ እስያ እና ናይጄሪያ በማስፋት አማራጮችን ፈጥሯል። በዚህም መሰረት፣ በቢሊየነሩ አሊኮ ዳንጎቴ ከሚተዳደረው የናይጄሪያው 'ዳንጎቴ ፔትሮሊየም ሪፋይነሪ' 120,000 ሜትሪክ ቶን የአቪዬሽን (የአውሮፕላን) እና የናፍጣ ነዳጅ በተሳካ ሁኔታ በ3 መርከቦች ወደ ጅቡቲ ሆራይዘን ተርሚናል ተጓጉዟል። ከዚህ ውስጥ 80,000 ሜትሪክ ቶኑ የአውሮፕላን ነዳጅ ነው።
ባለፉት አራት አስርት ዓመታት የነዳጅ ማጓጓዝ ስራውን በብቸኝነት ሲያከናውን የቆየው የኢትዮጵያ የነዳጅ አቅራቢ ድርጅት (EPSE) ሲሆን፣ አሁን ግን መንግስት ዘርፉን ክፍት በማድረግ የግል ባለሀብቶች፣ ዓለም አቀፍ ድርጅቶች እና የዲፕሎማቲክ ማህበረሰቡ በራሳቸው የውጭ ምንዛሬ ነዳጅ ማስገባት የሚችሉበትን መመሪያ አውጥቷል።
ኢትዮጵያ ነዳጅ የማታመርት በመሆኗ የገቢ ንግድ በጀቷን ሩብ ያህል ለነዳጅ የምታውል ሲሆን፣ በመጪው በጀት ዓመት የነዳጅ ወጪዋ እስከ 6 ቢሊዮን ዶላር ሊደርስ እንደሚችል የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ ለፓርላማው መግለጻቸውን በዘ-ሐበሻ ዜና መዘገባችን ይታወሳል። መንግስት በያዘው የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ መሰረት፣ የነዳጅ ድጎማን ቀስ በቀስ ለመቀነስ በማቀድ በመጪው በጀት ዓመት ለዘርፉ 20 ቢሊዮን ብር ብቻ የድጎማ በጀት አቅርቧል፤ ይህም ካለፈው ዓመት ጋር ሲነጻጸር ከፍተኛ ቅናሽ ያሳየ ነው።
7 hours ago
በአማራጭ የህፃናት እንክብካቤ ላደጉ ወጣቶች የተዘጋጀዉ የመጀመሪያው የስፖርት ፌስቲቫል ተጠናቀቀ!
#fastmereja I በአማራጭ የህፃናት እንክብካቤና ማሳደጊያ ተቋማት ውስጥ አድገው ለወጡ ወጣቶች የተዘጋጀው እና ላለፉት ሁለት ሳምንታት ሲካሄድ የቆየው የመጀመሪያው የስፖርት ፌስቲቫል የፍፃሜ ውድድር በዛሬዉ እለት በአዲስ አበባ በድምቀት ተጠናቋል።
ይህ የስፖርት ፌስቲቫል የተዘጋጀው ወጣቶቹ ከነበሩባቸው የማሳደጊያ ተቋማት ከወጡ በኋላ የሚገጥሟቸውን ዘርፈ-ብዙ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተግዳሮቶች በጋራ ለመጋፈጥ ባቋቋሙት ብሔራዊ ጥምረት አማካኝነት ሲሆን፣ መርሃ-ግብሩም በዴንማርክ መንግስት የሚደገፈዉ የ"Leave No Youth Behind" (ማንንም ወጣት ወደኋላ አንተዉም) ፕሮጀክት አካል መሆኑ ታዉቋል።
የብሔራዊ አማራጭ የህፃናት እንክብካቤ አድገው የወጡ ወጣቶች ማህበር ጥምረት የሚዲያ እና ኮሙኒኬሽን ሀላፊ አቶ ምስክር ታደሰ እንደገለጹት፤ የዚህ ስፖርታዊ ውድድር ዋና ዓላማ ወጣቶቹ እርስ በርስ እንዲገናኙ፣ ጤናቸውን እንዲጠብቁ እና ትስስራቸውን ይበልጥ እንዲያጠናክሩ ለማድረግ መሆኑን ገልፀዋል።
በተጨማሪም ወጣቶች ከማሳደጊያ ተቋማት ከወጡ በኋላ የሚያጋጥሟቸውን እንደ ስራ አጥነት እና የመኖሪያ ቤት ችግር ያሉ ፈተናዎችን በጋራ ለመፍታት እንዲሁም ወጣቶቹ እርስ በርስ ጠንካራ ትስስር(Network) እንዲፈጥሩ እና ወደፊት በጋራ ለሚቆሙላቸው መብቶች፣ የፖሊሲ ተፅዕኖ ማሳደርን ጨምሮ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ለመምከር ትልቅ መድረክ መፍጠሩን አቶ ምስክር አክለው አብራርተዋል።
በወንዶች የእግር ኳስ እና በሴቶች የመረብ ኳስ (ቮሊቦል) ውድድሮች በተካሄዱበት በዚህ ፌስቲቫል ላይ በርካታ የወጣቶች ማህበራት የተሳተፉ ሲሆን፤ የዓለም አካባቢ ጥበቃ ቀንን በማስመልከትም በዕለቱ የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር ተከናውኗል።
በፌስቲቫሉ ላይ የኤስ ኦ ኤስ (SOS) ህፃናት መንደር ወጣቶችን ያቀፈው “አልሙናይ ዩዝ አሶሴሽን'፣ የሰላም የህፃናት መንደር ወጣቶች ማህበር(ሰላም ፍሩትስ)፣ እንዲሁም እንደ ኮልፌ፣ ክበበ ፀሀይ እና ቀጨኔ ካሉ የመንግስት ማሳደጊያ ተቋማት የወጡ ወጣቶች የመሰረቱት “ፎር ኬ ኬር ሊቨርስ ቻሪቲ አሶሴሽን' የተሳተፉ ሲሆን፤ የአዲስ አበባ ወጣቶች ማህበር ደግሞ በክብር ተጋባዥነት ተገኝቷል።
በኢትዮጵያ የኤስ ኦ ኤስ (SOS) ህጻናት መንደሮች የአዲስ አበባ እና ዙሪያዋ ፕሮግራሞች ዳይሬክተር አቶ አለም ጌታቸው በበኩላቸው፤ ተቋማቸው ለዚህ የወጣቶች ጥምረት መመስረትና ለፌስቲቫሉ መሳካት የፋይናንስ እንዲሁም የቴክኒክ ድጋፍ ማድረጉን ገልጸዋል።
ድጋፉ በዴንማርክ መንግስት የገንዘብ እገዛ በሚተገበረው ሊቭ ኖ ዩዝ ቢሀይንድ(Leave No Youth Behind) ፕሮጀክት አማካኝነት የተደረገ ሲሆን፣ ዋና ዓላማውም ወጣቶቹ ተነቃቅተው ለራሳቸው መብት እንዲቆሙና የፖሊሲ ተፅዕኖ መፍጠር እንዲችሉ ማገዝ እንደሆነ አስረድተዋል።
በመሆኑም ይህንን መሰል የስፖርት መርሃ-ግብሮችን በየወሩ እንዲያካሂዱ፣ በፌስቲቫል ደረጃ ደግሞ በየስድስት ወሩ ወይም ባልተቻለ ሁኔታ በዓመት አንድ ጊዜ በቋሚነት እንዲያዘጋጁ ተቋማቸው ሁለንተናዊ እገዛ ማድረጉን እንደሚቀጥልበት አረጋግጠዋል።
#fastmereja I በአማራጭ የህፃናት እንክብካቤና ማሳደጊያ ተቋማት ውስጥ አድገው ለወጡ ወጣቶች የተዘጋጀው እና ላለፉት ሁለት ሳምንታት ሲካሄድ የቆየው የመጀመሪያው የስፖርት ፌስቲቫል የፍፃሜ ውድድር በዛሬዉ እለት በአዲስ አበባ በድምቀት ተጠናቋል።
ይህ የስፖርት ፌስቲቫል የተዘጋጀው ወጣቶቹ ከነበሩባቸው የማሳደጊያ ተቋማት ከወጡ በኋላ የሚገጥሟቸውን ዘርፈ-ብዙ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተግዳሮቶች በጋራ ለመጋፈጥ ባቋቋሙት ብሔራዊ ጥምረት አማካኝነት ሲሆን፣ መርሃ-ግብሩም በዴንማርክ መንግስት የሚደገፈዉ የ"Leave No Youth Behind" (ማንንም ወጣት ወደኋላ አንተዉም) ፕሮጀክት አካል መሆኑ ታዉቋል።
የብሔራዊ አማራጭ የህፃናት እንክብካቤ አድገው የወጡ ወጣቶች ማህበር ጥምረት የሚዲያ እና ኮሙኒኬሽን ሀላፊ አቶ ምስክር ታደሰ እንደገለጹት፤ የዚህ ስፖርታዊ ውድድር ዋና ዓላማ ወጣቶቹ እርስ በርስ እንዲገናኙ፣ ጤናቸውን እንዲጠብቁ እና ትስስራቸውን ይበልጥ እንዲያጠናክሩ ለማድረግ መሆኑን ገልፀዋል።
በተጨማሪም ወጣቶች ከማሳደጊያ ተቋማት ከወጡ በኋላ የሚያጋጥሟቸውን እንደ ስራ አጥነት እና የመኖሪያ ቤት ችግር ያሉ ፈተናዎችን በጋራ ለመፍታት እንዲሁም ወጣቶቹ እርስ በርስ ጠንካራ ትስስር(Network) እንዲፈጥሩ እና ወደፊት በጋራ ለሚቆሙላቸው መብቶች፣ የፖሊሲ ተፅዕኖ ማሳደርን ጨምሮ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ለመምከር ትልቅ መድረክ መፍጠሩን አቶ ምስክር አክለው አብራርተዋል።
በወንዶች የእግር ኳስ እና በሴቶች የመረብ ኳስ (ቮሊቦል) ውድድሮች በተካሄዱበት በዚህ ፌስቲቫል ላይ በርካታ የወጣቶች ማህበራት የተሳተፉ ሲሆን፤ የዓለም አካባቢ ጥበቃ ቀንን በማስመልከትም በዕለቱ የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር ተከናውኗል።
በፌስቲቫሉ ላይ የኤስ ኦ ኤስ (SOS) ህፃናት መንደር ወጣቶችን ያቀፈው “አልሙናይ ዩዝ አሶሴሽን'፣ የሰላም የህፃናት መንደር ወጣቶች ማህበር(ሰላም ፍሩትስ)፣ እንዲሁም እንደ ኮልፌ፣ ክበበ ፀሀይ እና ቀጨኔ ካሉ የመንግስት ማሳደጊያ ተቋማት የወጡ ወጣቶች የመሰረቱት “ፎር ኬ ኬር ሊቨርስ ቻሪቲ አሶሴሽን' የተሳተፉ ሲሆን፤ የአዲስ አበባ ወጣቶች ማህበር ደግሞ በክብር ተጋባዥነት ተገኝቷል።
በኢትዮጵያ የኤስ ኦ ኤስ (SOS) ህጻናት መንደሮች የአዲስ አበባ እና ዙሪያዋ ፕሮግራሞች ዳይሬክተር አቶ አለም ጌታቸው በበኩላቸው፤ ተቋማቸው ለዚህ የወጣቶች ጥምረት መመስረትና ለፌስቲቫሉ መሳካት የፋይናንስ እንዲሁም የቴክኒክ ድጋፍ ማድረጉን ገልጸዋል።
ድጋፉ በዴንማርክ መንግስት የገንዘብ እገዛ በሚተገበረው ሊቭ ኖ ዩዝ ቢሀይንድ(Leave No Youth Behind) ፕሮጀክት አማካኝነት የተደረገ ሲሆን፣ ዋና ዓላማውም ወጣቶቹ ተነቃቅተው ለራሳቸው መብት እንዲቆሙና የፖሊሲ ተፅዕኖ መፍጠር እንዲችሉ ማገዝ እንደሆነ አስረድተዋል።
በመሆኑም ይህንን መሰል የስፖርት መርሃ-ግብሮችን በየወሩ እንዲያካሂዱ፣ በፌስቲቫል ደረጃ ደግሞ በየስድስት ወሩ ወይም ባልተቻለ ሁኔታ በዓመት አንድ ጊዜ በቋሚነት እንዲያዘጋጁ ተቋማቸው ሁለንተናዊ እገዛ ማድረጉን እንደሚቀጥልበት አረጋግጠዋል።
8 hours ago
የባሕር ዳር ዓለም አቀፍ ስታዲየም እድሳት ተጠናቆ ወደ ውድድር ሊመለስ መሆኑ ተገለጸ
የባሕር ዳር ዓለም ከባህር ዳር ከተማ ስታዲየም በቅርቡ ወደ ስፖርታዊ ውድድሮች እንደሚመለስ የባሕር ዳር ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ጎሹ እንዳላማው አስታወቁ።
ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባው ይህንን የገለጹት በከተማዋ በደመቀ ሁኔታ በተካሄደው የ1ኛው የኢትዮጵያ 10 ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ ሩጫ ውድድር መዝጊያ ስነስርዓት ላይ ተገኝተው ባስተላለፉት መልዕክት ነው።
የስታዲየሙን ወቅታዊ ሁኔታ በተመለከተ ማብራሪያ የሰጡት ጎሹ እንዳላማው የባሕር ዳር ዓለም አቀፍ ስታዲየም የእድሳት ሥራ በአሁኑ ወቅት እየተጠናቀቀ መሆኑን ጠቁመው፣ ስታዲየሙ በቅርቡ ዓለም አቀፍ ስፖርታዊ ውድድሮችን ማስተናገድ በሚችልበት ቁመና ላይ እንደሚገኝ አረጋግጠዋል።
ከተማዋ ያሏትን ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁ ሆቴሎችና አዳዲስ እየተገነቡ ያሉ መስተንግዶዎችን ያነሱት ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባው ይህ መሰረተልማት ስታዲየሙንና ባህር ዳርን ሁሉ የተሟላላት ዘመናዊ የቱሪዝምና የስፖርት ከተማ እንደሚያደርጋት ገልጸዋል።
በሌላ በኩል በከተማዋ የተካሄደውን የጎዳና ላይ ሩጫ ውድድር አስመልክቶ ባደረጉት ንግግር ውድድሩ የባሕር ዳር ከተማ አስተማማኝ የሰላም ከተማ መሆኗን በተግባር ያረጋገጠበት መድረክ መሆኑን አስገንዝበዋል።
ውድድሩ በባሕር ዳር እንዲካሄድ ውሳኔ ላስተላለፉና በቦታው ተገኝተው ለታደሙት የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን አመራሮችም የከተማ አስተዳደሩን ምስጋና አቅርበዋል።
#አሐዱ
የባሕር ዳር ዓለም ከባህር ዳር ከተማ ስታዲየም በቅርቡ ወደ ስፖርታዊ ውድድሮች እንደሚመለስ የባሕር ዳር ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ጎሹ እንዳላማው አስታወቁ።
ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባው ይህንን የገለጹት በከተማዋ በደመቀ ሁኔታ በተካሄደው የ1ኛው የኢትዮጵያ 10 ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ ሩጫ ውድድር መዝጊያ ስነስርዓት ላይ ተገኝተው ባስተላለፉት መልዕክት ነው።
የስታዲየሙን ወቅታዊ ሁኔታ በተመለከተ ማብራሪያ የሰጡት ጎሹ እንዳላማው የባሕር ዳር ዓለም አቀፍ ስታዲየም የእድሳት ሥራ በአሁኑ ወቅት እየተጠናቀቀ መሆኑን ጠቁመው፣ ስታዲየሙ በቅርቡ ዓለም አቀፍ ስፖርታዊ ውድድሮችን ማስተናገድ በሚችልበት ቁመና ላይ እንደሚገኝ አረጋግጠዋል።
ከተማዋ ያሏትን ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁ ሆቴሎችና አዳዲስ እየተገነቡ ያሉ መስተንግዶዎችን ያነሱት ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባው ይህ መሰረተልማት ስታዲየሙንና ባህር ዳርን ሁሉ የተሟላላት ዘመናዊ የቱሪዝምና የስፖርት ከተማ እንደሚያደርጋት ገልጸዋል።
በሌላ በኩል በከተማዋ የተካሄደውን የጎዳና ላይ ሩጫ ውድድር አስመልክቶ ባደረጉት ንግግር ውድድሩ የባሕር ዳር ከተማ አስተማማኝ የሰላም ከተማ መሆኗን በተግባር ያረጋገጠበት መድረክ መሆኑን አስገንዝበዋል።
ውድድሩ በባሕር ዳር እንዲካሄድ ውሳኔ ላስተላለፉና በቦታው ተገኝተው ለታደሙት የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን አመራሮችም የከተማ አስተዳደሩን ምስጋና አቅርበዋል።
#አሐዱ
Sponsored by
Surafel
10 hours ago
በቆጂ ከተማ የ2018 ኢትዮ ቴሌኮም ታላቁ ሩጫን በስኬት አጠናቀቀች
#fastmereja I ለአምስተኛ ጊዜ የተካሄደውን 12 ኪሎ ሜትር የሚሸፍነውን የ2018 ኢትዮ ቴሌኮም ታላቁ የቦቆጂ ሩጫ በስኬት ተጠናቀቀ።
በቦቆጂ ስታድየም መነሻና መድረሻውን ባደረገው የዛሬው ውድድር በወንዶች የኦሮሚያ ኮንስትራክሽን አትሌት የሆነው ማሞ ሐጫሉ ቀዳሚ ሲሆን፣ አማን ቃዲ እና አልዬ ቃሲም 2ኛ እና 3ኛ ደረጃን ይዘዋል። በሴቶች ደግሞ የአሰላ አትሌቲክስ ክለብ ተወዳዳሪዋ ማህሌት ካሳሁን ስታሸንፍ፣ ኪያ ፍስሃ እና ድርቤ ኢርኮ ተከታትለው በመግባት የ2ኛ እና 3ኛ ደረጃን ተቆጣጥረዋል።
የ'ልወቅሽ ኢትዮጵያ ክላሲክስ’ ተከታታይ ውድድር አካል በሆነው በዚህ መርሃ ግብር ላይ የ15 ዓመት በታች የታዳጊዎች ሻምፕዮናም የተካሄደ ሲሆን፣ በተጨማሪም የ11 ዓመት በታች እና የህጻናት ውድድሮች ተካሂደዋል።
ከ2500 በላይ የአካባቢው ነዋሪዎች እና ከአዲስ አበባ የተጓዙ ከ70 በላይ ሯጮች የተሳተፉበት ይህ ውድድር በአርሲ አባቶች ምርቃት እና በብሔራዊ መዝሙር ተጀምሯል።
የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዲኤታ አቶ መኪዩ ሙሐመድ፣ የቱሪዝም ሚኒስቴር ሚኒስትር ዲኤታ እንደገና አበበ (ዶ/ር) እና የኦሮሚያ ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ሮዛ ቢያ፣ የአርሲ ዞን አስተዳዳሪ አቶ ኢብራሂም ከድር እና የቦቆጂ ከተማ ከንቲባን ብርሃነ ነገሰ ጨምሮ በርካታ የመንግስት ከፍተኛ ኃላፊዎች በቦታው ተገኝተዋል።
#fastmereja I ለአምስተኛ ጊዜ የተካሄደውን 12 ኪሎ ሜትር የሚሸፍነውን የ2018 ኢትዮ ቴሌኮም ታላቁ የቦቆጂ ሩጫ በስኬት ተጠናቀቀ።
በቦቆጂ ስታድየም መነሻና መድረሻውን ባደረገው የዛሬው ውድድር በወንዶች የኦሮሚያ ኮንስትራክሽን አትሌት የሆነው ማሞ ሐጫሉ ቀዳሚ ሲሆን፣ አማን ቃዲ እና አልዬ ቃሲም 2ኛ እና 3ኛ ደረጃን ይዘዋል። በሴቶች ደግሞ የአሰላ አትሌቲክስ ክለብ ተወዳዳሪዋ ማህሌት ካሳሁን ስታሸንፍ፣ ኪያ ፍስሃ እና ድርቤ ኢርኮ ተከታትለው በመግባት የ2ኛ እና 3ኛ ደረጃን ተቆጣጥረዋል።
የ'ልወቅሽ ኢትዮጵያ ክላሲክስ’ ተከታታይ ውድድር አካል በሆነው በዚህ መርሃ ግብር ላይ የ15 ዓመት በታች የታዳጊዎች ሻምፕዮናም የተካሄደ ሲሆን፣ በተጨማሪም የ11 ዓመት በታች እና የህጻናት ውድድሮች ተካሂደዋል።
ከ2500 በላይ የአካባቢው ነዋሪዎች እና ከአዲስ አበባ የተጓዙ ከ70 በላይ ሯጮች የተሳተፉበት ይህ ውድድር በአርሲ አባቶች ምርቃት እና በብሔራዊ መዝሙር ተጀምሯል።
የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዲኤታ አቶ መኪዩ ሙሐመድ፣ የቱሪዝም ሚኒስቴር ሚኒስትር ዲኤታ እንደገና አበበ (ዶ/ር) እና የኦሮሚያ ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ሮዛ ቢያ፣ የአርሲ ዞን አስተዳዳሪ አቶ ኢብራሂም ከድር እና የቦቆጂ ከተማ ከንቲባን ብርሃነ ነገሰ ጨምሮ በርካታ የመንግስት ከፍተኛ ኃላፊዎች በቦታው ተገኝተዋል።
11 hours ago
የገዳ ሥርዓት የሕዝቡን የወደፊት እጣ ፈንታ የሚቀርጽ በመሆኑ እንዲጠበቅ ይሰራል - አቶ ሽመልስ አብዲሳ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 7፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የገዳ ሥርዓት የዛሬውን ህያው ማህበራዊ ህይወትና የሕዝቡን የወደፊት እጣ ፈንታ የሚቀርጽ በመሆኑ ይበልጥ እንዲበለጽግና እንዲጠበቅ በትኩረት ይሰራል አሉ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳ።
71ኛው የቱለማ ኦሮሞ ገዳ የስልጣን ርክክብ በሸገር ከተማ ዳካ ኮራ አርዳ ጂላ በድምቀት ተካሂዷል።
በዚህም መሠረት የሜልባ አባ ገዳ ጎበና ሆላ የስልጣን ዘመናቸውን አጠናቀው ለሙደና አባ ገዳ ጌቱ ተሊላ የስልጣን ርክክብ አድርገዋል።
ከቀናት በፊት በዳካ ኮራ የተሰባሰቡ አባ ገዳዎችና በተለያዩ የገዳ ሥርዓት እርከኖች ውስጥ የሚገኙ የማህበረሰብ ክፍሎች የተለያዩ ባህላዊና ሃይማኖታዊ ሥርዓቶችን ሲያከናውኑ ቆይተዋል።
በየስምንት ዓመቱ በሚካሄደው የገዳ የስልጣን ሽግግር ደንብ መሠረት ዛሬ ከገዳ ሜልባ ወደ ገዳ ሙደና የአለንጌ ሽግግር ተደርጓል።
በሥነ ሥርዓቱ ላይ የተገኙት አቶ ሽመልስ አብዲሳ ባስተላለፉት መልዕክት÷ የገዳ ሥርዓት ለኦሮሞ ሕዝብ አንድነት ዋነኛ መሠረት በመሆኑ እሴቶቹን ይበልጥ ማጠናከርና ማስቀጠል እንደሚገባ ገልጸዋል።
የክልሉ መንግሥት ባከናወነው የባህል ሕዳሴ ከዚህ ቀደም ተረስተውና ተጥለው የነበሩ የኦሮሞ ባህሎችና እሴቶች ዳግም እንዲያንሰራሩና እንዲገነቡ አድርጓል ብለዋል።
ይህንኑ ለማሳካትም ከታችኛው የትምህርት እርከን ጀምሮ የገዳ ሥርዓት በሥርዓተ ትምህርት ውስጥ እንደ አንድ የትምህርት አይነት እንዲሰጥ መደረጉንና ትውልዱን በገዳ ሥርዓት እሴቶች ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።
የክልሉ መንግሥት ከሰጣቸው ቀዳሚ ትኩረቶች መካከል አንዱ የኦሮሞን ሕዝብ ጥንታዊ ባህል፣ እሴትና ማንነት ማልማት እንዲሁም ጠንካራ ተቋማዊ አሰራር መዘርጋት መሆኑንም አመልክተዋል።
ይህን ጥንታዊ እውቀት ማስቀጠል፣ ታሪካዊ ትረካዎችን ማስተካከል፣ እሴቶቹን ለኢኮኖሚ እድገት፣ ለኪነጥበብ፣ ለሚዲያ፣ ለስነ-ጽሁፍና ለእውቀት ምንጭነት ማዋል እንዲሁም ራሱን የቻለና ከተጨባጩ የዓለም ሁኔታ ጋር የተላመደ ትውልድ መፍጠር የክልሉ መንግሥት የትኩረት አቅጣጫዎች መሆናቸውን አብራርተዋል።
በዚህ የቱለማ ገዳ የአላንጌ (የስልጣን ሽግግር) ባህላዊ ሥነ ሥርዓት ላይ የጨፌ ኦሮሚያ አፈ ጉባኤ ሳዳ አብዱራህማን፣ የሸገር ከተማ ከፍተኛ አመራሮች፣ አባገዳዎች፣ ሃደ ሲንቄዎች እንዲሁም የተለያዩ የማህበረሰብ አባላት መገኘታቸውን ኢዜአ ዘግቧል።
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 7፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የገዳ ሥርዓት የዛሬውን ህያው ማህበራዊ ህይወትና የሕዝቡን የወደፊት እጣ ፈንታ የሚቀርጽ በመሆኑ ይበልጥ እንዲበለጽግና እንዲጠበቅ በትኩረት ይሰራል አሉ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳ።
71ኛው የቱለማ ኦሮሞ ገዳ የስልጣን ርክክብ በሸገር ከተማ ዳካ ኮራ አርዳ ጂላ በድምቀት ተካሂዷል።
በዚህም መሠረት የሜልባ አባ ገዳ ጎበና ሆላ የስልጣን ዘመናቸውን አጠናቀው ለሙደና አባ ገዳ ጌቱ ተሊላ የስልጣን ርክክብ አድርገዋል።
ከቀናት በፊት በዳካ ኮራ የተሰባሰቡ አባ ገዳዎችና በተለያዩ የገዳ ሥርዓት እርከኖች ውስጥ የሚገኙ የማህበረሰብ ክፍሎች የተለያዩ ባህላዊና ሃይማኖታዊ ሥርዓቶችን ሲያከናውኑ ቆይተዋል።
በየስምንት ዓመቱ በሚካሄደው የገዳ የስልጣን ሽግግር ደንብ መሠረት ዛሬ ከገዳ ሜልባ ወደ ገዳ ሙደና የአለንጌ ሽግግር ተደርጓል።
በሥነ ሥርዓቱ ላይ የተገኙት አቶ ሽመልስ አብዲሳ ባስተላለፉት መልዕክት÷ የገዳ ሥርዓት ለኦሮሞ ሕዝብ አንድነት ዋነኛ መሠረት በመሆኑ እሴቶቹን ይበልጥ ማጠናከርና ማስቀጠል እንደሚገባ ገልጸዋል።
የክልሉ መንግሥት ባከናወነው የባህል ሕዳሴ ከዚህ ቀደም ተረስተውና ተጥለው የነበሩ የኦሮሞ ባህሎችና እሴቶች ዳግም እንዲያንሰራሩና እንዲገነቡ አድርጓል ብለዋል።
ይህንኑ ለማሳካትም ከታችኛው የትምህርት እርከን ጀምሮ የገዳ ሥርዓት በሥርዓተ ትምህርት ውስጥ እንደ አንድ የትምህርት አይነት እንዲሰጥ መደረጉንና ትውልዱን በገዳ ሥርዓት እሴቶች ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።
የክልሉ መንግሥት ከሰጣቸው ቀዳሚ ትኩረቶች መካከል አንዱ የኦሮሞን ሕዝብ ጥንታዊ ባህል፣ እሴትና ማንነት ማልማት እንዲሁም ጠንካራ ተቋማዊ አሰራር መዘርጋት መሆኑንም አመልክተዋል።
ይህን ጥንታዊ እውቀት ማስቀጠል፣ ታሪካዊ ትረካዎችን ማስተካከል፣ እሴቶቹን ለኢኮኖሚ እድገት፣ ለኪነጥበብ፣ ለሚዲያ፣ ለስነ-ጽሁፍና ለእውቀት ምንጭነት ማዋል እንዲሁም ራሱን የቻለና ከተጨባጩ የዓለም ሁኔታ ጋር የተላመደ ትውልድ መፍጠር የክልሉ መንግሥት የትኩረት አቅጣጫዎች መሆናቸውን አብራርተዋል።
በዚህ የቱለማ ገዳ የአላንጌ (የስልጣን ሽግግር) ባህላዊ ሥነ ሥርዓት ላይ የጨፌ ኦሮሚያ አፈ ጉባኤ ሳዳ አብዱራህማን፣ የሸገር ከተማ ከፍተኛ አመራሮች፣ አባገዳዎች፣ ሃደ ሲንቄዎች እንዲሁም የተለያዩ የማህበረሰብ አባላት መገኘታቸውን ኢዜአ ዘግቧል።
14 hours ago
በአዲሱ በጀት ዓመት የመንግስት ሠራተኞች የደመወዝ ጭማሪ ይደረግ እንደሆነ በግልጽ እንዲታወቅ ተጠየቀ
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባካሄደው 5ኛ ዓመት 25ኛ መደበኛ ስብሰባው፤ የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ የፌደራል መንግስትን የ2019 በጀት ዓመት ረቂቅ በጀት በተመለከተ ከምክር ቤቱ አባላት ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል።
ጥያቄያቸውን ለምክር ቤቱ ካቀረቡት አባላት መካከል የአብን (የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ) ፓርቲን ወክለው የምክር ቤት አባል የሆኑት ዶክተር ደሳለኝ ጫኔ ይገኙበታል።
ዶክተር ደሳለኝ በጥያቄያቸው፤ መንግስት ለ2019 በጀት ዓመት ለመንግስት ሠራተኞች የደመወዝ ጭማሪ ያደርጋል ወይ? የሚለው ጉዳይ በግልጽ እንዲታወቅ ጠይቀዋል።
የምክር ቤት አባሉ ጥያቄውን ባቀረቡበት ወቅት ባለፈው ዓመት የታዘቡትን አጋጣሚ በማስታወስ፤ "ባለፈው ዓመት ተመሳሳይ ጥያቄ ለምክር ቤቱ አቅርቤ 'የደመወዝ ጭማሪ የለም' የሚል ምላሽ ከተሰጠኝ ከአንድ ወር በኋላ ጭማሪ ተደርጓል" ብለዋል። በመቀጠልም "ዘንድሮስ ጭማሪ የለም ካሉኝ ከአንድ ወር በኋላ ጭማሪ ይኖራል ወይ?" ሲሉ በሚኒስትሩ አገላለጽ ላይ ያላቸውን ጥርጣሬ በፈገግታ የታጀበ ጥያቄ በማስከተል ሰንዝረዋል።
ለቀረበው ጥያቄ ምላሽ የሰጡት የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ፤ መንግስት ቀደም ሲል በሁለት ዙር የደመወዝ ጭማሪ ማድረጉን ጠቅሰዋል።
ይሁን እንጂ በአሁኑ ወቅት በክልሎች በኩል በፐርሰንት ተሰርቶ የቀረበው የደመወዝ ጭማሪ ተመን እና ለጉዳዩ ከተመደበው በጀት ጋር ባለመመጣጠኑ ምክንያት፣ አሁንም ድረስ ተጨማሪ የማጥራትና የማስተካከል ሥራዎች እየተሰሩ መሆኑን ሚኒስትሩ ለአባላቱ አስገንዝበዋል።
Seledadotio
Seledadotio
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባካሄደው 5ኛ ዓመት 25ኛ መደበኛ ስብሰባው፤ የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ የፌደራል መንግስትን የ2019 በጀት ዓመት ረቂቅ በጀት በተመለከተ ከምክር ቤቱ አባላት ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል።
ጥያቄያቸውን ለምክር ቤቱ ካቀረቡት አባላት መካከል የአብን (የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ) ፓርቲን ወክለው የምክር ቤት አባል የሆኑት ዶክተር ደሳለኝ ጫኔ ይገኙበታል።
ዶክተር ደሳለኝ በጥያቄያቸው፤ መንግስት ለ2019 በጀት ዓመት ለመንግስት ሠራተኞች የደመወዝ ጭማሪ ያደርጋል ወይ? የሚለው ጉዳይ በግልጽ እንዲታወቅ ጠይቀዋል።
የምክር ቤት አባሉ ጥያቄውን ባቀረቡበት ወቅት ባለፈው ዓመት የታዘቡትን አጋጣሚ በማስታወስ፤ "ባለፈው ዓመት ተመሳሳይ ጥያቄ ለምክር ቤቱ አቅርቤ 'የደመወዝ ጭማሪ የለም' የሚል ምላሽ ከተሰጠኝ ከአንድ ወር በኋላ ጭማሪ ተደርጓል" ብለዋል። በመቀጠልም "ዘንድሮስ ጭማሪ የለም ካሉኝ ከአንድ ወር በኋላ ጭማሪ ይኖራል ወይ?" ሲሉ በሚኒስትሩ አገላለጽ ላይ ያላቸውን ጥርጣሬ በፈገግታ የታጀበ ጥያቄ በማስከተል ሰንዝረዋል።
ለቀረበው ጥያቄ ምላሽ የሰጡት የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ፤ መንግስት ቀደም ሲል በሁለት ዙር የደመወዝ ጭማሪ ማድረጉን ጠቅሰዋል።
ይሁን እንጂ በአሁኑ ወቅት በክልሎች በኩል በፐርሰንት ተሰርቶ የቀረበው የደመወዝ ጭማሪ ተመን እና ለጉዳዩ ከተመደበው በጀት ጋር ባለመመጣጠኑ ምክንያት፣ አሁንም ድረስ ተጨማሪ የማጥራትና የማስተካከል ሥራዎች እየተሰሩ መሆኑን ሚኒስትሩ ለአባላቱ አስገንዝበዋል።
Seledadotio
Seledadotio
14 hours ago
ታዋቂዋ የአትሌቶች መፍለቂያ ቦቆጂ ከተማ የልወቅሽ የኢትዮጵያ ክላሲክ 2018 የሩጫ ውድድርን በደመቀ ሁኔታ ማስተናገድ ጀመረች
#ethiopia | የበርካታ የዓለምና የኦሊምፒክ ሻምፒዮኖችን በማፍራት በዓለም አቀፍ ደረጃ በግንባር ቀደምትነት የምትጠቀሰው የቦቆጂ ከተማ፣ የቱሪዝም ሚኒስቴር ከታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ጋር በመሆን ያዘጋጀውን ልወቅሽ የኢትዮጵያ ክላሲክ ታላቅ የሩጫ ውድድር በዛሬው ዕለት ማስተናገድ ጀምራለች።
ውድድሩ መነሻና መድረሻውን ታሪካዊው የቦቆጂ ስታዲየም ላይ ያደረገ ሲሆን፣ ከ100 በላይ አንጋፋና ፕሮፌሽናል አትሌቶች፣ ከ2 ሺህ 500 በላይ የቦቆጂ ከተማ ነዋሪዎች እንዲሁም ከአዲስ አበባ የተጓዙ ከ70 በላይ የስፖርቱ አፍቃሪያን ተሳታፊ ሆነዋል።
ይህ ትልቅ ስፖርታዊ መርሃ ግብር የአትሌቲክስ ስፖርትን ለማሳደግ ከሚኖረው ሚና ባሻገር፣ የቦቆጂን ከተማ የቱሪዝም መስህቦችና አቅሞች ለሀገር ውስጥና ለውጭ ሀገር ጎብኝዎች በሰፊው ለማስተዋወቅ ታላቅ ዕድል የፈጠረ ነው።
የመጀመሪያው ምዕራፉ በደብረ ብርሃን ከተማ ተጀምሮ አሁን በቦቆጂ ይፋዊ ጉዞውን የቀጠለው ይህ መርሃ ግብር፣ በኢትዮጵያ የስፖርት ቱሪዝም ልማት ላይ አዲስ ምዕራፍ የከፈተ ክስተት ሆኗል።
በዚህ ደማቅ የማስጀመሪያ ዝግጅት ላይ የኢፌዲሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የንግድና ቱሪዝም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባላት፣ የቱሪዝም ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር እንደገና አበበ፣ የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ አቶ መኪዩ መሀመድ፣ የአርሲ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ኢብራሒም ከድር እና የቦቆጂ ከተማ ከንቲባ ወይዘሮ ብርሃኔ ነገሰ ተገኝተዋል።
በተጨማሪም ሌሎች ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች፣ የቱሪዝም ዘርፍ ተወካዮች፣ ታዋቂ ተፅዕኖ ፈጣሪ ግለሰቦችና የብዙኃን መገናኛ ባለሙያዎች በከተማዋ በመገኘት መርሃ ግብሩን ታድመዋል።
#bekoji #ethiopianclassic #greatethiopianrun #sportstourism #tourismethiopia #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | የበርካታ የዓለምና የኦሊምፒክ ሻምፒዮኖችን በማፍራት በዓለም አቀፍ ደረጃ በግንባር ቀደምትነት የምትጠቀሰው የቦቆጂ ከተማ፣ የቱሪዝም ሚኒስቴር ከታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ጋር በመሆን ያዘጋጀውን ልወቅሽ የኢትዮጵያ ክላሲክ ታላቅ የሩጫ ውድድር በዛሬው ዕለት ማስተናገድ ጀምራለች።
ውድድሩ መነሻና መድረሻውን ታሪካዊው የቦቆጂ ስታዲየም ላይ ያደረገ ሲሆን፣ ከ100 በላይ አንጋፋና ፕሮፌሽናል አትሌቶች፣ ከ2 ሺህ 500 በላይ የቦቆጂ ከተማ ነዋሪዎች እንዲሁም ከአዲስ አበባ የተጓዙ ከ70 በላይ የስፖርቱ አፍቃሪያን ተሳታፊ ሆነዋል።
ይህ ትልቅ ስፖርታዊ መርሃ ግብር የአትሌቲክስ ስፖርትን ለማሳደግ ከሚኖረው ሚና ባሻገር፣ የቦቆጂን ከተማ የቱሪዝም መስህቦችና አቅሞች ለሀገር ውስጥና ለውጭ ሀገር ጎብኝዎች በሰፊው ለማስተዋወቅ ታላቅ ዕድል የፈጠረ ነው።
የመጀመሪያው ምዕራፉ በደብረ ብርሃን ከተማ ተጀምሮ አሁን በቦቆጂ ይፋዊ ጉዞውን የቀጠለው ይህ መርሃ ግብር፣ በኢትዮጵያ የስፖርት ቱሪዝም ልማት ላይ አዲስ ምዕራፍ የከፈተ ክስተት ሆኗል።
በዚህ ደማቅ የማስጀመሪያ ዝግጅት ላይ የኢፌዲሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የንግድና ቱሪዝም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባላት፣ የቱሪዝም ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር እንደገና አበበ፣ የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ አቶ መኪዩ መሀመድ፣ የአርሲ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ኢብራሒም ከድር እና የቦቆጂ ከተማ ከንቲባ ወይዘሮ ብርሃኔ ነገሰ ተገኝተዋል።
በተጨማሪም ሌሎች ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች፣ የቱሪዝም ዘርፍ ተወካዮች፣ ታዋቂ ተፅዕኖ ፈጣሪ ግለሰቦችና የብዙኃን መገናኛ ባለሙያዎች በከተማዋ በመገኘት መርሃ ግብሩን ታድመዋል።
#bekoji #ethiopianclassic #greatethiopianrun #sportstourism #tourismethiopia #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
14 hours ago
በአቶ ግርማ ዋቄ የሚመራው የኡጋንዳ አየር መንገድ ከቦይንግ ኩባንያ ጋር የ982 ሚሊዮን ዶላር ግዙፍ ስምምነት አደረገ
#ethiopia | የኡጋንዳ ብሔራዊ አየር መንገድ 10 ዘመናዊ አውሮፕላኖችን ለመግዛት የሚያስችለውንና 982 ሚሊዮን ዶላር የሚያወጣውን ታሪካዊ የጋራ ስምምነት ከታዋቂው የቦይንግ ኩባንያ ጋር መፈራረሙ ታውቋል።
ይህ ከፍተኛ መዋዕለ ንዋይ የፈሰሰበት ግዢ አየር መንገዱ በፈረንጆቹ 2019 አገልግሎቱን በድጋሚ ከጀመረበት ጊዜ አንስቶ የፈጸመው ትልቁ የአውሮፕላን ኢንቨስትመንት ተብሎ ተመዝግቧል።
የስምምነቱ ማጠናቀቂያ የፊርማ ሥነ ሥርዓት በኢንቴቤ ቤተ መንግሥት የተከናወነ ሲሆን፣ የኡጋንዳው ፕሬዚዳንት ዮዌሪ ሙሴቬኒ በክብር ታዛቢነት ተገኝተዋል።
ይህንን ታላቅ ውል በኡጋንዳ አየር መንገድ ስም የፈረሙት ጊዜያዊ ዋና ሥራ አስፈጻሚው አቶ ግርማ ዋቄ ሲሆኑ፣ በቦይንግ ኩባንያ በኩል ደግሞ የአፍሪካ የሽያጭ ኃላፊው አቶ አንበሴ ይትባረክ ውሉን አጽድቀዋል።
በገንዘብ ሲሰላ በግምት 3 ነጥብ 7 ትሪሊዮን የኡጋንዳ ሺሊንግ የሚያወጣው ይህ የ10 አውሮፕላኖች ግዢ ጥቅል አራት የቦይንግ 787-9 ድሪምላይነር እና አራት የቦይንግ 737 ማክስ የመንገደኞች አውሮፕላኖችን ያካተተ ነው።
በተጨማሪም አንድ ወደ ጭነት አገልግሎት የተቀየረ ቦይንግ 767 እንዲሁም ሌላ አንድ ወደ ጭነት አጓጓዥነት የተቀየረ ቦይንግ 737 አውሮፕላን በስምምነቱ ውስጥ ተካተዋል።
ይህ የተወሰደው ስትራቴጂካዊ እርምጃ አየር መንገዱ ዓለም አቀፍ የመንገደኞች በረራውን በከፍተኛ ደረጃ ለማስፋፋት ከመጣር ባለፈ፣ በጭነት ትራንስፖርት ዘርፍም ጠንካራና ተወዳዳሪ ሆኖ ለመውጣት ያለውን ጽኑ ፍላጎት የሚያሳይ ነው።
በያፌት ገብረሕይወት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#ugandaairlines #boeing #aviationnews #girmawake #business #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | የኡጋንዳ ብሔራዊ አየር መንገድ 10 ዘመናዊ አውሮፕላኖችን ለመግዛት የሚያስችለውንና 982 ሚሊዮን ዶላር የሚያወጣውን ታሪካዊ የጋራ ስምምነት ከታዋቂው የቦይንግ ኩባንያ ጋር መፈራረሙ ታውቋል።
ይህ ከፍተኛ መዋዕለ ንዋይ የፈሰሰበት ግዢ አየር መንገዱ በፈረንጆቹ 2019 አገልግሎቱን በድጋሚ ከጀመረበት ጊዜ አንስቶ የፈጸመው ትልቁ የአውሮፕላን ኢንቨስትመንት ተብሎ ተመዝግቧል።
የስምምነቱ ማጠናቀቂያ የፊርማ ሥነ ሥርዓት በኢንቴቤ ቤተ መንግሥት የተከናወነ ሲሆን፣ የኡጋንዳው ፕሬዚዳንት ዮዌሪ ሙሴቬኒ በክብር ታዛቢነት ተገኝተዋል።
ይህንን ታላቅ ውል በኡጋንዳ አየር መንገድ ስም የፈረሙት ጊዜያዊ ዋና ሥራ አስፈጻሚው አቶ ግርማ ዋቄ ሲሆኑ፣ በቦይንግ ኩባንያ በኩል ደግሞ የአፍሪካ የሽያጭ ኃላፊው አቶ አንበሴ ይትባረክ ውሉን አጽድቀዋል።
በገንዘብ ሲሰላ በግምት 3 ነጥብ 7 ትሪሊዮን የኡጋንዳ ሺሊንግ የሚያወጣው ይህ የ10 አውሮፕላኖች ግዢ ጥቅል አራት የቦይንግ 787-9 ድሪምላይነር እና አራት የቦይንግ 737 ማክስ የመንገደኞች አውሮፕላኖችን ያካተተ ነው።
በተጨማሪም አንድ ወደ ጭነት አገልግሎት የተቀየረ ቦይንግ 767 እንዲሁም ሌላ አንድ ወደ ጭነት አጓጓዥነት የተቀየረ ቦይንግ 737 አውሮፕላን በስምምነቱ ውስጥ ተካተዋል።
ይህ የተወሰደው ስትራቴጂካዊ እርምጃ አየር መንገዱ ዓለም አቀፍ የመንገደኞች በረራውን በከፍተኛ ደረጃ ለማስፋፋት ከመጣር ባለፈ፣ በጭነት ትራንስፖርት ዘርፍም ጠንካራና ተወዳዳሪ ሆኖ ለመውጣት ያለውን ጽኑ ፍላጎት የሚያሳይ ነው።
በያፌት ገብረሕይወት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#ugandaairlines #boeing #aviationnews #girmawake #business #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
1 day ago
በ25 ድምፅ ወደ ምክር ቤት፤ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ እጅግ ዝቅተኛ በሆነ የድምፅ ቁጥር የተመረጡ ተፎካካሪ ዕጩዎች መኖራቸው ታወቀ!
ምርጫ ቦርድ ባወጣቸው ተከታታይ መግለጫዎች ያጸደቃቸው ከፊል ውጤቶች፣ በርካታ ተፎካካሪ በሌለባቸው የምርጫ ክልሎች የሚወዳደሩ የተቃዋሚ ዕጩዎች እጅግ ዝቅተኛ በሆነ የመራጮች ድምፅ ወደ ምክር ቤቶች መግባታቸውን አሳይተዋል።
ከእነዚህ መካከል ለድሬዳዋ ከተማ ምክር ቤት በኩርቱ የምርጫ ክልል የተመረጡት የነፃነትና እኩልነት ፓርቲ ዕጩ አቶ ጀማል ኡመር ኢብራሂም፣ ከተመዘገቡት 2,204 መራጮች መካከል ያገኙት ድምፅ 25 ብቻ (1% ገደማ) እንደሆነ ተገልጿል።
በጀሎበጂና የምርጫ ክልልም የአዲስ ትውልድ ፓርቲ ተወካዩ አቶ ረመዳን መሐመድ ሰኢድ 200 ድምፅ (3%) ብቻ በማግኘት ወደ ምክር ቤት መግባት ችለዋል።ለዚህም ዋነኛው ምክንያት በእነዚህ የምርጫ ክልሎች ከወንበሮቹ ቁጥር እኩል ከሆኑት ዕጩዎች ውጪ ሌላ ተወዳዳሪ ፓርቲ ባለመኖሩ ነው።
እስካሁን ከተመረጡት 8 ተቃዋሚዎች መካከል እውነተኛ የአብላጫ ድምፅ (ከ50% በላይ) ያገኙት የኦብነግ ተወካይ አቶ መሀሙድ ሀሰን (73%) እና የአብን ዕጩ አቶ ጣሂር መሀመድ (59%) ብቻ ሲሆኑ፣ ቀሪዎቹ 6ቱ ዕጩዎች የኢዜማውን መሪ አቶ እዮብ መሳፍንትን (42%) ጨምሮ ከ50% በታች ድምፅ አግኝተዋል።ስምንቱም የተቃዋሚ ወኪሎች ያሸነፏቸው ወንበሮች ብልፅግና ፓርቲ ውክልናን ለማሳደግ በሚል ሆነ ብሎ ዕጩ ያላቀረበባቸው መሆኑ ታውቋል።
ኢትዮጵያ ኢንሳይደር
Seledadotio
Seledadotio
ምርጫ ቦርድ ባወጣቸው ተከታታይ መግለጫዎች ያጸደቃቸው ከፊል ውጤቶች፣ በርካታ ተፎካካሪ በሌለባቸው የምርጫ ክልሎች የሚወዳደሩ የተቃዋሚ ዕጩዎች እጅግ ዝቅተኛ በሆነ የመራጮች ድምፅ ወደ ምክር ቤቶች መግባታቸውን አሳይተዋል።
ከእነዚህ መካከል ለድሬዳዋ ከተማ ምክር ቤት በኩርቱ የምርጫ ክልል የተመረጡት የነፃነትና እኩልነት ፓርቲ ዕጩ አቶ ጀማል ኡመር ኢብራሂም፣ ከተመዘገቡት 2,204 መራጮች መካከል ያገኙት ድምፅ 25 ብቻ (1% ገደማ) እንደሆነ ተገልጿል።
በጀሎበጂና የምርጫ ክልልም የአዲስ ትውልድ ፓርቲ ተወካዩ አቶ ረመዳን መሐመድ ሰኢድ 200 ድምፅ (3%) ብቻ በማግኘት ወደ ምክር ቤት መግባት ችለዋል።ለዚህም ዋነኛው ምክንያት በእነዚህ የምርጫ ክልሎች ከወንበሮቹ ቁጥር እኩል ከሆኑት ዕጩዎች ውጪ ሌላ ተወዳዳሪ ፓርቲ ባለመኖሩ ነው።
እስካሁን ከተመረጡት 8 ተቃዋሚዎች መካከል እውነተኛ የአብላጫ ድምፅ (ከ50% በላይ) ያገኙት የኦብነግ ተወካይ አቶ መሀሙድ ሀሰን (73%) እና የአብን ዕጩ አቶ ጣሂር መሀመድ (59%) ብቻ ሲሆኑ፣ ቀሪዎቹ 6ቱ ዕጩዎች የኢዜማውን መሪ አቶ እዮብ መሳፍንትን (42%) ጨምሮ ከ50% በታች ድምፅ አግኝተዋል።ስምንቱም የተቃዋሚ ወኪሎች ያሸነፏቸው ወንበሮች ብልፅግና ፓርቲ ውክልናን ለማሳደግ በሚል ሆነ ብሎ ዕጩ ያላቀረበባቸው መሆኑ ታውቋል።
ኢትዮጵያ ኢንሳይደር
Seledadotio
Seledadotio
1 day ago
‹‹ብልጽግና እና ሕውሓት ኤርትራን በጋራ ለማጥቃት ተነጋግረው ነበር›› ሻብያ
የኤርትራ መንግስት አዲስ እና ያልተሰማ ትርክት ይዞ ብቅ ብሏል፡፡ አቶ ጌታቸው ረዳ እና አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን ከሰሞኑ አልጀዚራ ላይ ያጋሩትን ጽሁፍ ተከትሎ ከአስመራ ምላሽ ተሰጥቷል፡፡ የአገሪቱ ማስታወቂያ ሚኒስትር አቶ የማነ ገብረመስቀል፣ በጽሁፉ ላይ የቀረቡትን ሁሉንም ክሶች አጣጥለዋል፡፡
የማነ ገብረመስቀል በትዊተር ገጻቸው ላይ ባሰፈሩት ምላሽ የባለሥልጣናትን ንግግር "በሐሰት፣ በማታለልና በተሳሳተ መረጃ የተሞላ" ሲሉ አጣጥለውታል። አቶ የማነ ምላሻቸው በመቀጠል ይልቁንም ዛሬ ክስ እያቀረቡብን ያሉት አካላት "የፕሪቶሪያው ስምምነት ከመፈረሙ ከጥቂት ወራት በፊት በጅቡቲ እና ሲሸልስ በሚስጥር ተገናኝተው በኤርትራ ላይ የጋራ ወረራ ለመፈጸም ሲዶልቱ ነበር" በማለት ከዚህ በፊት ያልተሰማ ሌላ አዲስ ትርክት ይዘው መጥተዋል።
አንዳፍታ
Seledadotio
Seledadotio
የኤርትራ መንግስት አዲስ እና ያልተሰማ ትርክት ይዞ ብቅ ብሏል፡፡ አቶ ጌታቸው ረዳ እና አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን ከሰሞኑ አልጀዚራ ላይ ያጋሩትን ጽሁፍ ተከትሎ ከአስመራ ምላሽ ተሰጥቷል፡፡ የአገሪቱ ማስታወቂያ ሚኒስትር አቶ የማነ ገብረመስቀል፣ በጽሁፉ ላይ የቀረቡትን ሁሉንም ክሶች አጣጥለዋል፡፡
የማነ ገብረመስቀል በትዊተር ገጻቸው ላይ ባሰፈሩት ምላሽ የባለሥልጣናትን ንግግር "በሐሰት፣ በማታለልና በተሳሳተ መረጃ የተሞላ" ሲሉ አጣጥለውታል። አቶ የማነ ምላሻቸው በመቀጠል ይልቁንም ዛሬ ክስ እያቀረቡብን ያሉት አካላት "የፕሪቶሪያው ስምምነት ከመፈረሙ ከጥቂት ወራት በፊት በጅቡቲ እና ሲሸልስ በሚስጥር ተገናኝተው በኤርትራ ላይ የጋራ ወረራ ለመፈጸም ሲዶልቱ ነበር" በማለት ከዚህ በፊት ያልተሰማ ሌላ አዲስ ትርክት ይዘው መጥተዋል።
አንዳፍታ
Seledadotio
Seledadotio
Sponsored by
Surafel
1 day ago
ወጣቶች በሚያደርጉት የነቃ ተሳትፎ ሀገር ይገነባል - አቶ አረጋ ከበደ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 6፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ በወቅታዊ የልማትና የሰላም ሥራዎች ዙሪያ ከወጣቶች ጋር በባሕር ዳር ተወያይተዋል፡፡
በመድረኩ የሰላም እና የልማት ሥራዎችን በትጋት በማከናወን ሀገርን ወደ ላቀ ከፍታ ለመውሰድ የወጣቶች ሚና ምን መሆን እንዳለበት ተነስቷል።
በዚሁ ወቅት አቶ አረጋ ከበደ ፥ በወጣቶች ሁለንተናዊና የነቃ ተሳትፎ ሀገር ይገነባል፤ የሕዝብ ሰላም በዘላቂነት ይረጋገጣል፤ የተጀመሩ የልማት ሥራዎችም ከዳር ይደርሳሉ ብለዋል።
የባሕር ዳር ከተማ ብሎም የክልሉ ወጣቶች በትላልቅ ሀገራዊ ሁነቶች በንቃት የሚሳተፉ፣ በውጤትም አጅበው ሥራዎችን የሚፈጽሙ ናቸው ማለታቸውን አሚኮ ዘግቧል፡፡
ወጣቶች በተለይም 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላሙ የተጠበቀ፣ ፍትሐዊ እና ዴሞክራሲያዊ እንዲሆን ሚናቸው ከፍተኛ እንደነበር አንስተው÷ ከመሪዎቻቸው ጋር በመተባበር የልማት ሥራዎችን እያከናወኑ እንደሚገኙ አንስተዋል።
ወጣቶች በሥራ ዕድል ተጠቃሚ እንዲሆኑና የራሳቸውን ብሎም የሀገራቸውን ኢኮኖሚያዊ ልዕልና እንዲያረጋግጡ እንሠራለን ነው ያሉት፡፡
ለሕዝብ ሰላምና ልማት የሚተጉ ወጣቶች የሀገር መሠረቶች ናቸው፤ ወጣቶች ሀገርን በሚጠቅሙ ዘርፎች ላይ ሁሉ በንቃት በመሳተፍ የልማት አርበኛ ሊሆኑ ይገባል ሲሉም አስገንዝበዋል፡፡
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 6፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ በወቅታዊ የልማትና የሰላም ሥራዎች ዙሪያ ከወጣቶች ጋር በባሕር ዳር ተወያይተዋል፡፡
በመድረኩ የሰላም እና የልማት ሥራዎችን በትጋት በማከናወን ሀገርን ወደ ላቀ ከፍታ ለመውሰድ የወጣቶች ሚና ምን መሆን እንዳለበት ተነስቷል።
በዚሁ ወቅት አቶ አረጋ ከበደ ፥ በወጣቶች ሁለንተናዊና የነቃ ተሳትፎ ሀገር ይገነባል፤ የሕዝብ ሰላም በዘላቂነት ይረጋገጣል፤ የተጀመሩ የልማት ሥራዎችም ከዳር ይደርሳሉ ብለዋል።
የባሕር ዳር ከተማ ብሎም የክልሉ ወጣቶች በትላልቅ ሀገራዊ ሁነቶች በንቃት የሚሳተፉ፣ በውጤትም አጅበው ሥራዎችን የሚፈጽሙ ናቸው ማለታቸውን አሚኮ ዘግቧል፡፡
ወጣቶች በተለይም 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላሙ የተጠበቀ፣ ፍትሐዊ እና ዴሞክራሲያዊ እንዲሆን ሚናቸው ከፍተኛ እንደነበር አንስተው÷ ከመሪዎቻቸው ጋር በመተባበር የልማት ሥራዎችን እያከናወኑ እንደሚገኙ አንስተዋል።
ወጣቶች በሥራ ዕድል ተጠቃሚ እንዲሆኑና የራሳቸውን ብሎም የሀገራቸውን ኢኮኖሚያዊ ልዕልና እንዲያረጋግጡ እንሠራለን ነው ያሉት፡፡
ለሕዝብ ሰላምና ልማት የሚተጉ ወጣቶች የሀገር መሠረቶች ናቸው፤ ወጣቶች ሀገርን በሚጠቅሙ ዘርፎች ላይ ሁሉ በንቃት በመሳተፍ የልማት አርበኛ ሊሆኑ ይገባል ሲሉም አስገንዝበዋል፡፡
2 days ago
በአዲሱ በጀት ዓመት የመንግስት ሠራተኞች የደመወዝ ጭማሪ ይደረግ እንደሆነ በግልጽ እንዲታወቅ ተጠየቀ
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባካሄደው 5ኛ ዓመት 25ኛ መደበኛ ስብሰባው፤ የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ የፌደራል መንግስትን የ2019 በጀት ዓመት ረቂቅ በጀት በተመለከተ ከምክር ቤቱ አባላት ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል።
ጥያቄያቸውን ለምክር ቤቱ ካቀረቡት አባላት መካከል የአብን (የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ) ፓርቲን ወክለው የምክር ቤት አባል የሆኑት ዶክተር ደሳለኝ ጫኔ ይገኙበታል።
ዶክተር ደሳለኝ በጥያቄያቸው፤ መንግስት ለ2019 በጀት ዓመት ለመንግስት ሠራተኞች የደመወዝ ጭማሪ ያደርጋል ወይ? የሚለው ጉዳይ በግልጽ እንዲታወቅ ጠይቀዋል።
የምክር ቤት አባሉ ጥያቄውን ባቀረቡበት ወቅት ባለፈው ዓመት የታዘቡትን አጋጣሚ በማስታወስ፤ "ባለፈው ዓመት ተመሳሳይ ጥያቄ ለምክር ቤቱ አቅርቤ 'የደመወዝ ጭማሪ የለም' የሚል ምላሽ ከተሰጠኝ ከአንድ ወር በኋላ ጭማሪ ተደርጓል" ብለዋል። በመቀጠልም "ዘንድሮስ ጭማሪ የለም ካሉኝ ከአንድ ወር በኋላ ጭማሪ ይኖራል ወይ?" ሲሉ በሚኒስትሩ አገላለጽ ላይ ያላቸውን ጥርጣሬ በፈገግታ የታጀበ ጥያቄ በማስከተል ሰንዝረዋል።
ለቀረበው ጥያቄ ምላሽ የሰጡት የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ፤ መንግስት ቀደም ሲል በሁለት ዙር የደመወዝ ጭማሪ ማድረጉን ጠቅሰዋል።
ይሁን እንጂ በአሁኑ ወቅት በክልሎች በኩል በፐርሰንት ተሰርቶ የቀረበው የደመወዝ ጭማሪ ተመን እና ለጉዳዩ ከተመደበው በጀት ጋር ባለመመጣጠኑ ምክንያት፣ አሁንም ድረስ ተጨማሪ የማጥራትና የማስተካከል ሥራዎች እየተሰሩ መሆኑን ሚኒስትሩ ለአባላቱ አስገንዝበዋል።
አቤል እስጢፋኖስ ethio fm 107.8
Seledadotio
Seledadotio
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባካሄደው 5ኛ ዓመት 25ኛ መደበኛ ስብሰባው፤ የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ የፌደራል መንግስትን የ2019 በጀት ዓመት ረቂቅ በጀት በተመለከተ ከምክር ቤቱ አባላት ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል።
ጥያቄያቸውን ለምክር ቤቱ ካቀረቡት አባላት መካከል የአብን (የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ) ፓርቲን ወክለው የምክር ቤት አባል የሆኑት ዶክተር ደሳለኝ ጫኔ ይገኙበታል።
ዶክተር ደሳለኝ በጥያቄያቸው፤ መንግስት ለ2019 በጀት ዓመት ለመንግስት ሠራተኞች የደመወዝ ጭማሪ ያደርጋል ወይ? የሚለው ጉዳይ በግልጽ እንዲታወቅ ጠይቀዋል።
የምክር ቤት አባሉ ጥያቄውን ባቀረቡበት ወቅት ባለፈው ዓመት የታዘቡትን አጋጣሚ በማስታወስ፤ "ባለፈው ዓመት ተመሳሳይ ጥያቄ ለምክር ቤቱ አቅርቤ 'የደመወዝ ጭማሪ የለም' የሚል ምላሽ ከተሰጠኝ ከአንድ ወር በኋላ ጭማሪ ተደርጓል" ብለዋል። በመቀጠልም "ዘንድሮስ ጭማሪ የለም ካሉኝ ከአንድ ወር በኋላ ጭማሪ ይኖራል ወይ?" ሲሉ በሚኒስትሩ አገላለጽ ላይ ያላቸውን ጥርጣሬ በፈገግታ የታጀበ ጥያቄ በማስከተል ሰንዝረዋል።
ለቀረበው ጥያቄ ምላሽ የሰጡት የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ፤ መንግስት ቀደም ሲል በሁለት ዙር የደመወዝ ጭማሪ ማድረጉን ጠቅሰዋል።
ይሁን እንጂ በአሁኑ ወቅት በክልሎች በኩል በፐርሰንት ተሰርቶ የቀረበው የደመወዝ ጭማሪ ተመን እና ለጉዳዩ ከተመደበው በጀት ጋር ባለመመጣጠኑ ምክንያት፣ አሁንም ድረስ ተጨማሪ የማጥራትና የማስተካከል ሥራዎች እየተሰሩ መሆኑን ሚኒስትሩ ለአባላቱ አስገንዝበዋል።
አቤል እስጢፋኖስ ethio fm 107.8
Seledadotio
Seledadotio
2 days ago
የአሜሪካዋ ግዛት ምክር ቤት ለአድዋ ድል መታሰቢያ ቀን ሰየመ
#fastmereja I በአሜሪካ፣ የፔንሲልቪኒያ ግዛት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፣ የአውሮፓዊያኑ 'መጋቢት 2' በግዛቱ የአድዋ ድል መታሰቢያ ቀን እንዲሆን የቀረበን የውሳኔ ሐሳብ በከፍተኛ ድምጽ አፀደቀ።
ይህ 'ኤችአር 441' የተሰኘው የውሳኔ ሐሳብ የፀደቀው ባለፈው ሳምንት በግዛቲቱ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በተደረገ የድምጽ አሰጣጥ ሥነ ሥርዓት ነው።
በአሜሪካ የግዛቶች ምክር ቤት አሠራር መሠረት፣ ይህ ውሳኔ በግዛቲቱ የሕግ መዝገብ ላይ የአድዋ ድል በይፋ ዕውቅና ያገኘበት ታሪካዊ ሰነድ ሆኖ በቋሚነት ይቀመጣል።
ይህ የውሳኔ ሐሳብ ረቂቅ፣ የአውሮፓውያኑ 'ማርች 2 ቀን 2026' የ130ኛ 'የአድዋ ድል ቀን' ሆኖ በፔንሲልቬኒያ ግዛት ዕውቅና እንዲሰጠው የሚደነግግ ነው።
ውሳኔው በሪፐብሊካን እና በዲሞክራቲክ ፓርቲ እንደራሴዎች በተሰጠ 195 ከፍተኛ የድጋፍ ድምጽ እና በ6 ተቃውሞ ብቻ ነው የፀደቀው።
ረቂቁ የቀረበው ከወራት በፊት ቢሆንም የምክር ቤቱን የውስጥ አሠራሮችን አልፎ፣ ውይይቶች ተደርገውበት ከቆየ በኋላ የውሳኔ ድምጽ የተሰጠበት ግን ባለፈው ሳምንት ነው።
''ኤችአር 441'' ረቂቅ የውሳኔ ሐሳቡን ለፔንሴልቬኒያ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ያቀረቡት የሰሜን ፊላደልፊያ ሜንገመሪ ካውንቲ፣ የሕዝብ ተወካይ የሆኑት ሴናተር ቤንጃሚን ሳንቼዝ ናቸው።
ቢቢሲ የፀደቀውን የውሳኔ ሐሳብ አስመልክቶ ተጨማሪ ማብራሪያ እንዲሰጡት ሴናተሩን በኢሜይል ጥያቄ አቅርቦላቸው የነበረ ሲሆን፣ ይህ ዘገባ እስኪጠናቀር ድረስ ምላሽ አልሰጡም።
ሆኖም እርሳቸው ረቂቁን ባቀረቡት ዕለት በምክር ቤቱ ባደረጉት ንግግር፣ አድዋ ለአፍሪካ አሜሪካዊያን ያለውን ታላቅ ትርጉም አውስተዋል።
የምክር ቤቱ አባል ሴናተር ቤንጃሚን ሳንቼዝ በዕለቱ በንባብ ባሰሙት የመክፈቻ ንግግር በዘመናዊ የዓለም ታሪክ ውስጥ አድዋ የማይናቅ ቦታ እንዳለው ካወሱ በኋላ "ኢትዮጵያዊው ንጉሥ ዳግማዊ ምንሊክ እና ባለቤታቸው ጣይቱ ብጡል በአመራር ሰጪነት አገራቸውን ከቅኝ ገዥ ተቀራማቾች" ማስጣላቸውን አብራርተዋል።
ይህም ለአፍሪካ አሜሪካዊያን፣ በአገረ ግዛቱ ውስጥ ለሚኖሩ ትውልደ ኢትዮጵያዊያን ሁሉ ታላቅ ኩራት ነው ብለዋል።
የፔንሲልቬኒያ ግዛት የተወካዮች ምክር ቤት በበኩሉ በድረ ገጹ ባሰፈረው ጽሑፍ አውሮፓውያን የአፍሪካ አገራትን ቅኝ ግዛት በያዙበት እና መቼም ነፃ የሚወጡ በማይመስልበት በዚያን ወቅት ኢትዮጵያ ነፃነቷን በማስከበር የአደዋ ድልን አድንቋል።
በዚህም ኢትዮጵያ ቅኝ ያልተገዛች ብቸኛዋ አፍሪካዊት አገር በመሆን በ19ኛው እና በ20ኛው ክፍለ ዘመን በነበሩ የዓለም ኃያላን ዕውቅና ማግኘቷን ገልጿል።
በመሆኑም የአውሮፓውያኑ መጋቢት 2 በፔንሲልቬኒያ ግዛት "የአድዋ ድል መታሰቢያ ቀን" እንዲሆን ውሳኔ ማሳለፉን አስታውቋል።
"የአድዋ ድል ቀንን በማክበር የአሜሪካን ታሪክንም እናከብራለን" ብሏል።
ምክር ቤቱ ያሳለፈውን ውሳኔ በኢትዮጵያ እና በአሜሪካ ግንኙነት ላይ የሚሠራው 'አሜሪካን ኢትዮጵያን ፐብሊክ አፌርስ ኮሚቴ' አወድሶታል።
"የፔንሲልቬኒያ ምክር ቤት በውሳኔው ከአድዋ የተቀሰመው ትምህርት ዛሬም ድረስ ወሳኝ መሆኑን የሚያሳይ ትልቅ መልዕክት አስተላልፏል። በዓለም ሚሊዮኖችን ለሚያነሳሳ እና ለሚያኮራ ለዚህ ታሪካዊ ቀን ዕውቅና በመስጠቱ እናመሰግናለን" ብሏል።
ኮሚቴው ኤችአር 441 ረቂቅ የውሳኔ ሐሳቡን ለፔንሴልቬኒያ ምክር ቤት ላቀረቡት የሕዝብ ተወካይ ቤንጃሚን ሳንቼዝም ምስጋናውን አቅርቧል።
በኮሎራዶ ግዛት የአውሮራ ከተማ ምክር ቤት እንደራሴ እና የሪፐብሊካን ፓርቲ አባል የሆኑት ትውልደ ኢትዮጵያዊው አቶ አምሳሉ ፀጋዬ ኤችአር 441' የተባለው ውሳኔ በምክር ቤቱ ባሉ ሁለቱም ፓርቲዎች [ ዲሞክራት እና ሪፐብሊካን] በከፍተኛ ድምጽ የጸደቀ መሆኑን ለቢቢሲ ተናግረዋል።
ውሳኔው የአውሮፓውያኑ መጋቢት 2 የኢትዮጵያ አርበኞች በ1896 በአድዋ ተራሮች የጣሊያንን ዘመናዊ ጦር ድል ያደረጉበትን ዕለት ለማስታወስ የተላለፈ መሆኑንም አክለዋል።
13 ሚሊዮን ሕዝብ በሚኖርባት ፔንሲልቬኒያ ግዛት በርካታ ትውልደ ኢትዮጵያን ፊላዴልፊያን ጨምሮ በሌሎች የግዛቲቱ ትልልቅ ከተሞች ውስጥ ይኖራሉ።
"የኢትዮጵያ ታሪክ በኢትዮጵያውያን ብቻ ተወስኖ የሚቀር አይደለም" ያሉት አቶ አምሳሉ፣ "ያ ታሪክ የአፍሪካውያን እና የጥቁር አሜሪካውያን ታሪክም ጭምር ነው" በማለት፣ የድል ቀኑ በፔንሲልቬኒያ ግዛት እንዲታሰብ መደረጉ ወርቃማ ዕድልን የሚፈጥር እንደሆነም ገልጸዋል።
የአድዋ ድል በተመሳሳይ እርሳቸው በተወከሉበት ኮሎራዶ ግዛት፣ አውሮራ ከተማ ምክር ቤትም ዕውቅና ተሰጥቶት 'የጥቁሮች ታሪክ ከሚዘከርበት ወር' ጋር ተጣምሮ የሚከበር በዓል እንደሆነም አስታውሰዋል።
ጉዳዩ ወደ ምክር ቤቱ ከመምጣቱ በፊት ከፍተኛ እንቅስቃሴ ሲደረግበት እንደነበር ያወሱት አቶ አምሳሉ "ይህ ታሪካዊ ድል ለኢትዮጵያውያን፣ ለአሜሪካውያን፣ ለጥቁሮች በሙሉ ትልቅ ዕድል ነው" ብለዋል።
በግዛቲቱ 'መጋቢት 2፣ 2026 'ለ130ኛው የዓድዋ በዓል' መታሰቢያ እንዲሆን ተወሰነ ሲባል ትርጉሙ ምንድነው? ለምንስ ውሳኔው ረዥም ጊዜን ሊወስድ ቻለ በሚል የተጠየቁት አቶ አምሳሉ፣ በምክር ቤት አሠራር የውሳኔ ሐሳቦች (ሪዞሉሽንስ) ብዙ ማለፍ ያለባቸው ሂደት ስላለ ነው ብለዋል።
'መጋቢት 2' የአድዋ ቀን መባሉ ደግሞ ለአንድ ጊዜና ለአንድ ዓመት ብቻ ሳይሆን ቋሚና ቀጣይ እንደሆነ አብራርተዋል።
ዕለቱ ለአድዋ ድል መሰየሙ በተግባር ምን ማለት እንደሆነ ተጠይቀው በግዛቲቱ ቀን መቁጠሪያ (ካላንደር) ውስጥ 'የአድዋ ቀን' ተብሎ ተካትቶ ታስቦ ይውላል። ይህም ትልቅ ትርጉም ያለው ተዕምርታዊ (ሲምቦሊክ) ነው' ብለዋል።
ሆኖም ውሳኔው በዚያው ግዛት ተፈፃሚ የሚሆን እንጂ ወደ ፌደራል የሚያመራ እንዳልሆነም አክለዋል።
ይሁንና አድዋ በበርካታ ግዛቶች ዕውቅና እያገኘ ከመጣ፣ ወደፊት ኢትዮ- አሜሪካውያን፣ ጥቁር አሜሪካውያን እና የተለያዩ አደረጃጀቶች ጉዳዩን በጊዜ ሂደት ወደ ፌደራል ይዘውት እንዲሄዱ አንዳች ዕድል ሊፈጥረ እንደሚችል ያላቸውን ተስፋ ተናግረዋል።
አድዋ ኢትዮጵያ በአፄ ምንሊክ እና ባለቤታቸው እቴጌ ጣይቱ አመራር ሰጪነት የጣሊያን ወራሪዎችን ድል በመምታት ሉዓላዊነቷን አስከብራ የቆየችበት እና በዓለም አቀፍ ደረጃ የጥቁር ሕዝቦች ነፃነት እና ፀረ-ቅኝ ግዛት ትግል ምልክት የሆነ ታሪካዊ ድል ነው።
ከአድዋ ድል በኋላ በርካታ አገራት የፀረ-ቅኝ ግዛት ተጋድሏቸውን በማጠናከር ለዓመታት በዘለቀ ትግል ነፃነታቸውን መቀዳጀት ችለዋል።
በአፍሪካ ሁለት አገራት ቅኝ አለመገዛታቸውን ታሪክ የሚያስረዳ ሲሆን፣ ኢትዮጵያ ራሷን ያስከበረችው አርበኞቿ ባደረጉ ትግል ነው።
በአድዋ ጦርነት በሺዎች የሚቆጠሩ የጣሊያን ሠራዊት አባላት ሲገደሉ ሌሎች ሺህዎች ደግሞ ተማርከዋል። መድፎችን ጨምሮ ከፍተኛ መጠን ያለው የጦር መሳሪያዎችም መማረካቸውን ታሪክ ያስረዳል።
በተጨማሪም የጣሊያንን ሠራዊት ከመሩት መኮንኖች መካከል ጄነራል አልቤርቶኒ ሲማረክ ዋና አዛዥ ጄነራል ባራቴሪ ሸሽቶ አምልጧል።
ኢትዮጵያ ይህንን ታሪካዊ ድል የተጎናፀፈችበትን የካቲት 23 ቀንን በየዓመቱ በደማቅ ታሪካዊ ሁነቶች ታከብራለች።
ባለፈው የካቲት ወርም 130ኛው የአድዋ ድል በዓል ተከብሯል። ዘገባው የቢቢሲ አማርኛ ነው
#fastmereja I በአሜሪካ፣ የፔንሲልቪኒያ ግዛት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፣ የአውሮፓዊያኑ 'መጋቢት 2' በግዛቱ የአድዋ ድል መታሰቢያ ቀን እንዲሆን የቀረበን የውሳኔ ሐሳብ በከፍተኛ ድምጽ አፀደቀ።
ይህ 'ኤችአር 441' የተሰኘው የውሳኔ ሐሳብ የፀደቀው ባለፈው ሳምንት በግዛቲቱ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በተደረገ የድምጽ አሰጣጥ ሥነ ሥርዓት ነው።
በአሜሪካ የግዛቶች ምክር ቤት አሠራር መሠረት፣ ይህ ውሳኔ በግዛቲቱ የሕግ መዝገብ ላይ የአድዋ ድል በይፋ ዕውቅና ያገኘበት ታሪካዊ ሰነድ ሆኖ በቋሚነት ይቀመጣል።
ይህ የውሳኔ ሐሳብ ረቂቅ፣ የአውሮፓውያኑ 'ማርች 2 ቀን 2026' የ130ኛ 'የአድዋ ድል ቀን' ሆኖ በፔንሲልቬኒያ ግዛት ዕውቅና እንዲሰጠው የሚደነግግ ነው።
ውሳኔው በሪፐብሊካን እና በዲሞክራቲክ ፓርቲ እንደራሴዎች በተሰጠ 195 ከፍተኛ የድጋፍ ድምጽ እና በ6 ተቃውሞ ብቻ ነው የፀደቀው።
ረቂቁ የቀረበው ከወራት በፊት ቢሆንም የምክር ቤቱን የውስጥ አሠራሮችን አልፎ፣ ውይይቶች ተደርገውበት ከቆየ በኋላ የውሳኔ ድምጽ የተሰጠበት ግን ባለፈው ሳምንት ነው።
''ኤችአር 441'' ረቂቅ የውሳኔ ሐሳቡን ለፔንሴልቬኒያ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ያቀረቡት የሰሜን ፊላደልፊያ ሜንገመሪ ካውንቲ፣ የሕዝብ ተወካይ የሆኑት ሴናተር ቤንጃሚን ሳንቼዝ ናቸው።
ቢቢሲ የፀደቀውን የውሳኔ ሐሳብ አስመልክቶ ተጨማሪ ማብራሪያ እንዲሰጡት ሴናተሩን በኢሜይል ጥያቄ አቅርቦላቸው የነበረ ሲሆን፣ ይህ ዘገባ እስኪጠናቀር ድረስ ምላሽ አልሰጡም።
ሆኖም እርሳቸው ረቂቁን ባቀረቡት ዕለት በምክር ቤቱ ባደረጉት ንግግር፣ አድዋ ለአፍሪካ አሜሪካዊያን ያለውን ታላቅ ትርጉም አውስተዋል።
የምክር ቤቱ አባል ሴናተር ቤንጃሚን ሳንቼዝ በዕለቱ በንባብ ባሰሙት የመክፈቻ ንግግር በዘመናዊ የዓለም ታሪክ ውስጥ አድዋ የማይናቅ ቦታ እንዳለው ካወሱ በኋላ "ኢትዮጵያዊው ንጉሥ ዳግማዊ ምንሊክ እና ባለቤታቸው ጣይቱ ብጡል በአመራር ሰጪነት አገራቸውን ከቅኝ ገዥ ተቀራማቾች" ማስጣላቸውን አብራርተዋል።
ይህም ለአፍሪካ አሜሪካዊያን፣ በአገረ ግዛቱ ውስጥ ለሚኖሩ ትውልደ ኢትዮጵያዊያን ሁሉ ታላቅ ኩራት ነው ብለዋል።
የፔንሲልቬኒያ ግዛት የተወካዮች ምክር ቤት በበኩሉ በድረ ገጹ ባሰፈረው ጽሑፍ አውሮፓውያን የአፍሪካ አገራትን ቅኝ ግዛት በያዙበት እና መቼም ነፃ የሚወጡ በማይመስልበት በዚያን ወቅት ኢትዮጵያ ነፃነቷን በማስከበር የአደዋ ድልን አድንቋል።
በዚህም ኢትዮጵያ ቅኝ ያልተገዛች ብቸኛዋ አፍሪካዊት አገር በመሆን በ19ኛው እና በ20ኛው ክፍለ ዘመን በነበሩ የዓለም ኃያላን ዕውቅና ማግኘቷን ገልጿል።
በመሆኑም የአውሮፓውያኑ መጋቢት 2 በፔንሲልቬኒያ ግዛት "የአድዋ ድል መታሰቢያ ቀን" እንዲሆን ውሳኔ ማሳለፉን አስታውቋል።
"የአድዋ ድል ቀንን በማክበር የአሜሪካን ታሪክንም እናከብራለን" ብሏል።
ምክር ቤቱ ያሳለፈውን ውሳኔ በኢትዮጵያ እና በአሜሪካ ግንኙነት ላይ የሚሠራው 'አሜሪካን ኢትዮጵያን ፐብሊክ አፌርስ ኮሚቴ' አወድሶታል።
"የፔንሲልቬኒያ ምክር ቤት በውሳኔው ከአድዋ የተቀሰመው ትምህርት ዛሬም ድረስ ወሳኝ መሆኑን የሚያሳይ ትልቅ መልዕክት አስተላልፏል። በዓለም ሚሊዮኖችን ለሚያነሳሳ እና ለሚያኮራ ለዚህ ታሪካዊ ቀን ዕውቅና በመስጠቱ እናመሰግናለን" ብሏል።
ኮሚቴው ኤችአር 441 ረቂቅ የውሳኔ ሐሳቡን ለፔንሴልቬኒያ ምክር ቤት ላቀረቡት የሕዝብ ተወካይ ቤንጃሚን ሳንቼዝም ምስጋናውን አቅርቧል።
በኮሎራዶ ግዛት የአውሮራ ከተማ ምክር ቤት እንደራሴ እና የሪፐብሊካን ፓርቲ አባል የሆኑት ትውልደ ኢትዮጵያዊው አቶ አምሳሉ ፀጋዬ ኤችአር 441' የተባለው ውሳኔ በምክር ቤቱ ባሉ ሁለቱም ፓርቲዎች [ ዲሞክራት እና ሪፐብሊካን] በከፍተኛ ድምጽ የጸደቀ መሆኑን ለቢቢሲ ተናግረዋል።
ውሳኔው የአውሮፓውያኑ መጋቢት 2 የኢትዮጵያ አርበኞች በ1896 በአድዋ ተራሮች የጣሊያንን ዘመናዊ ጦር ድል ያደረጉበትን ዕለት ለማስታወስ የተላለፈ መሆኑንም አክለዋል።
13 ሚሊዮን ሕዝብ በሚኖርባት ፔንሲልቬኒያ ግዛት በርካታ ትውልደ ኢትዮጵያን ፊላዴልፊያን ጨምሮ በሌሎች የግዛቲቱ ትልልቅ ከተሞች ውስጥ ይኖራሉ።
"የኢትዮጵያ ታሪክ በኢትዮጵያውያን ብቻ ተወስኖ የሚቀር አይደለም" ያሉት አቶ አምሳሉ፣ "ያ ታሪክ የአፍሪካውያን እና የጥቁር አሜሪካውያን ታሪክም ጭምር ነው" በማለት፣ የድል ቀኑ በፔንሲልቬኒያ ግዛት እንዲታሰብ መደረጉ ወርቃማ ዕድልን የሚፈጥር እንደሆነም ገልጸዋል።
የአድዋ ድል በተመሳሳይ እርሳቸው በተወከሉበት ኮሎራዶ ግዛት፣ አውሮራ ከተማ ምክር ቤትም ዕውቅና ተሰጥቶት 'የጥቁሮች ታሪክ ከሚዘከርበት ወር' ጋር ተጣምሮ የሚከበር በዓል እንደሆነም አስታውሰዋል።
ጉዳዩ ወደ ምክር ቤቱ ከመምጣቱ በፊት ከፍተኛ እንቅስቃሴ ሲደረግበት እንደነበር ያወሱት አቶ አምሳሉ "ይህ ታሪካዊ ድል ለኢትዮጵያውያን፣ ለአሜሪካውያን፣ ለጥቁሮች በሙሉ ትልቅ ዕድል ነው" ብለዋል።
በግዛቲቱ 'መጋቢት 2፣ 2026 'ለ130ኛው የዓድዋ በዓል' መታሰቢያ እንዲሆን ተወሰነ ሲባል ትርጉሙ ምንድነው? ለምንስ ውሳኔው ረዥም ጊዜን ሊወስድ ቻለ በሚል የተጠየቁት አቶ አምሳሉ፣ በምክር ቤት አሠራር የውሳኔ ሐሳቦች (ሪዞሉሽንስ) ብዙ ማለፍ ያለባቸው ሂደት ስላለ ነው ብለዋል።
'መጋቢት 2' የአድዋ ቀን መባሉ ደግሞ ለአንድ ጊዜና ለአንድ ዓመት ብቻ ሳይሆን ቋሚና ቀጣይ እንደሆነ አብራርተዋል።
ዕለቱ ለአድዋ ድል መሰየሙ በተግባር ምን ማለት እንደሆነ ተጠይቀው በግዛቲቱ ቀን መቁጠሪያ (ካላንደር) ውስጥ 'የአድዋ ቀን' ተብሎ ተካትቶ ታስቦ ይውላል። ይህም ትልቅ ትርጉም ያለው ተዕምርታዊ (ሲምቦሊክ) ነው' ብለዋል።
ሆኖም ውሳኔው በዚያው ግዛት ተፈፃሚ የሚሆን እንጂ ወደ ፌደራል የሚያመራ እንዳልሆነም አክለዋል።
ይሁንና አድዋ በበርካታ ግዛቶች ዕውቅና እያገኘ ከመጣ፣ ወደፊት ኢትዮ- አሜሪካውያን፣ ጥቁር አሜሪካውያን እና የተለያዩ አደረጃጀቶች ጉዳዩን በጊዜ ሂደት ወደ ፌደራል ይዘውት እንዲሄዱ አንዳች ዕድል ሊፈጥረ እንደሚችል ያላቸውን ተስፋ ተናግረዋል።
አድዋ ኢትዮጵያ በአፄ ምንሊክ እና ባለቤታቸው እቴጌ ጣይቱ አመራር ሰጪነት የጣሊያን ወራሪዎችን ድል በመምታት ሉዓላዊነቷን አስከብራ የቆየችበት እና በዓለም አቀፍ ደረጃ የጥቁር ሕዝቦች ነፃነት እና ፀረ-ቅኝ ግዛት ትግል ምልክት የሆነ ታሪካዊ ድል ነው።
ከአድዋ ድል በኋላ በርካታ አገራት የፀረ-ቅኝ ግዛት ተጋድሏቸውን በማጠናከር ለዓመታት በዘለቀ ትግል ነፃነታቸውን መቀዳጀት ችለዋል።
በአፍሪካ ሁለት አገራት ቅኝ አለመገዛታቸውን ታሪክ የሚያስረዳ ሲሆን፣ ኢትዮጵያ ራሷን ያስከበረችው አርበኞቿ ባደረጉ ትግል ነው።
በአድዋ ጦርነት በሺዎች የሚቆጠሩ የጣሊያን ሠራዊት አባላት ሲገደሉ ሌሎች ሺህዎች ደግሞ ተማርከዋል። መድፎችን ጨምሮ ከፍተኛ መጠን ያለው የጦር መሳሪያዎችም መማረካቸውን ታሪክ ያስረዳል።
በተጨማሪም የጣሊያንን ሠራዊት ከመሩት መኮንኖች መካከል ጄነራል አልቤርቶኒ ሲማረክ ዋና አዛዥ ጄነራል ባራቴሪ ሸሽቶ አምልጧል።
ኢትዮጵያ ይህንን ታሪካዊ ድል የተጎናፀፈችበትን የካቲት 23 ቀንን በየዓመቱ በደማቅ ታሪካዊ ሁነቶች ታከብራለች።
ባለፈው የካቲት ወርም 130ኛው የአድዋ ድል በዓል ተከብሯል። ዘገባው የቢቢሲ አማርኛ ነው
2 days ago
በ2019 በጀት ዓመት አንድ ነጥብ 817 ትሪሊዮን ብር ገቢ ለመሰብሰብ ዕቅድ ተይዟል
#ethiopia | በአዲሱ 2019 በጀት ዓመት አንድ ነጥብ 817 ትሪሊዮን ብር ገቢ ለመሰብሰብ መታቀዱን የገንዘብ ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡
የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ የ2019 በጀት ዓመት የበጀት መግለጫ ማብራሪያ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሲያቀርቡ እንደገለጹት፤ በ2019 በጀት ዓመት የፌዴራል መንግሥት በጥቅሉ አንድ ነጥብ 817 ትሪሊዮን ብር ገቢ ለመሰብሰብ አቅዷል፡፡
ይህ የገቢ ዕቅድ በ2018 በጀት ዓመት ይሰበሰባል ተብሎ ከተገመተው ጠቅላላ ገቢ አንጻር የ17 ነጥብ 4 በመቶ ዕድገት እንዳለው ጠቁመው፤ የ2019 በጀት ዓመት በጀትን 88 ነጥብ 7 በመቶውን ከታክስና ታክስ ካልሆኑ ገቢዎች ለመሰብሰብ መታቀዱንም ጠቁመዋል።
የታክስ ገቢ ዕቅዱን ለማሳካትም በታክስ ፖሊሲና በታክስ አስተዳደር ረገድ የተያዙ ማሻሻያዎችን፣ የታክስ ዲጂታላይዜሽንና የኤክሳይዝ ስታምፕ አሠራርን በተጠናከረ ሁኔታ ተግባራዊ ለማድረግ ዝግጅት ተደርጓል፡፡
ለ2019 በጀት ዓመት የተቀመጠው የተጣራ የበጀት ጉድለት መንግሥት በተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው የተረጋጋ ኢኮኖሚ ለመፍጠር ከተቀመጠው ግብ ጋር የተጣጣመ እንደሆነም ነው የገለጹት፡፡
ከብሔራዊ ባንክ በጀት ጉድለት መሸፈኛ የሚወሰደው ብድር ሙሉ በሙሉ ቆሟል ያሉት ሚኒስትሩ፤ ይህም የዋጋ ንረትን ወደ ነጠላ አሃዝ ለማውረድ ማገዙን ተናግረዋል፡፡
የብሔራዊ ባንክ የፖሊሲ ወለድ ምጣኔ ተግባራዊ በመደረጉ ዘመናዊ የገንዘብ ፖሊሲውን የሚያጠናክሩ በርካታ ለውጦች እየተመዘገቡ ሲሆን፤ ብሔራዊ ባንክ የዘረጋውን ዘመናዊ የገንዘብ ፖሊሲ ለማስጠበቅ የተጀመሩ ሥራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ ብለዋል፡፡
የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው የዋጋ ንረት ለማረጋጋት ትልቅ ድርሻ እንዳለው የገለጹት ሚኒስትሩ፤ መንግሥት በምግብ ዘይትና በመሠረታዊ ሸቀጦች እንዲሁም መድኃኒቶችን በተመሳሳይ የድጎማ በጀት በመመደብ ዝቅተኛ ገቢ ላላቸው የኅብረተሰብ ክፍሎች ድጋፍ እያደረገ እንደሆነ ገልጸዋል፡፡
በቀጣዩ የ2019 በጀት ዓመት የ10 ነጥብ 1 በመቶ የኢኮኖሚ ዕድገት እንደሚመዘገብ ግምት የተቀመጠ ሲሆን፤ በኢኮኖሚ እድገቱ ኢንደስትሪ፤ አገልግሎት ዘርፍና ግብርና ከፍተኛውን ድርሻ ይይዛሉ፡፡
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #የኢትዮጵያ_ፕሬስ_ድርጅት #ጋዜጣፕላስ #በጀት2019 #ታክስ #የልማትእቅድ #አፍሪካ #gazette_plus
#ethiopia | በአዲሱ 2019 በጀት ዓመት አንድ ነጥብ 817 ትሪሊዮን ብር ገቢ ለመሰብሰብ መታቀዱን የገንዘብ ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡
የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ የ2019 በጀት ዓመት የበጀት መግለጫ ማብራሪያ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሲያቀርቡ እንደገለጹት፤ በ2019 በጀት ዓመት የፌዴራል መንግሥት በጥቅሉ አንድ ነጥብ 817 ትሪሊዮን ብር ገቢ ለመሰብሰብ አቅዷል፡፡
ይህ የገቢ ዕቅድ በ2018 በጀት ዓመት ይሰበሰባል ተብሎ ከተገመተው ጠቅላላ ገቢ አንጻር የ17 ነጥብ 4 በመቶ ዕድገት እንዳለው ጠቁመው፤ የ2019 በጀት ዓመት በጀትን 88 ነጥብ 7 በመቶውን ከታክስና ታክስ ካልሆኑ ገቢዎች ለመሰብሰብ መታቀዱንም ጠቁመዋል።
የታክስ ገቢ ዕቅዱን ለማሳካትም በታክስ ፖሊሲና በታክስ አስተዳደር ረገድ የተያዙ ማሻሻያዎችን፣ የታክስ ዲጂታላይዜሽንና የኤክሳይዝ ስታምፕ አሠራርን በተጠናከረ ሁኔታ ተግባራዊ ለማድረግ ዝግጅት ተደርጓል፡፡
ለ2019 በጀት ዓመት የተቀመጠው የተጣራ የበጀት ጉድለት መንግሥት በተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው የተረጋጋ ኢኮኖሚ ለመፍጠር ከተቀመጠው ግብ ጋር የተጣጣመ እንደሆነም ነው የገለጹት፡፡
ከብሔራዊ ባንክ በጀት ጉድለት መሸፈኛ የሚወሰደው ብድር ሙሉ በሙሉ ቆሟል ያሉት ሚኒስትሩ፤ ይህም የዋጋ ንረትን ወደ ነጠላ አሃዝ ለማውረድ ማገዙን ተናግረዋል፡፡
የብሔራዊ ባንክ የፖሊሲ ወለድ ምጣኔ ተግባራዊ በመደረጉ ዘመናዊ የገንዘብ ፖሊሲውን የሚያጠናክሩ በርካታ ለውጦች እየተመዘገቡ ሲሆን፤ ብሔራዊ ባንክ የዘረጋውን ዘመናዊ የገንዘብ ፖሊሲ ለማስጠበቅ የተጀመሩ ሥራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ ብለዋል፡፡
የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው የዋጋ ንረት ለማረጋጋት ትልቅ ድርሻ እንዳለው የገለጹት ሚኒስትሩ፤ መንግሥት በምግብ ዘይትና በመሠረታዊ ሸቀጦች እንዲሁም መድኃኒቶችን በተመሳሳይ የድጎማ በጀት በመመደብ ዝቅተኛ ገቢ ላላቸው የኅብረተሰብ ክፍሎች ድጋፍ እያደረገ እንደሆነ ገልጸዋል፡፡
በቀጣዩ የ2019 በጀት ዓመት የ10 ነጥብ 1 በመቶ የኢኮኖሚ ዕድገት እንደሚመዘገብ ግምት የተቀመጠ ሲሆን፤ በኢኮኖሚ እድገቱ ኢንደስትሪ፤ አገልግሎት ዘርፍና ግብርና ከፍተኛውን ድርሻ ይይዛሉ፡፡
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #የኢትዮጵያ_ፕሬስ_ድርጅት #ጋዜጣፕላስ #በጀት2019 #ታክስ #የልማትእቅድ #አፍሪካ #gazette_plus
Sponsored by
Surafel
2 days ago
የብሔራዊ አልኮል ቡድን የሴቶች ቮሊቦል ፕሪሚየር ሊግን በበላይነት አጠናቀቀ
#ethiopia | የ2018 ዓ.ም የደራባ ሚድሮክ ሲሚንቶ የሴቶች ቮሊቦል ፕሪሚየር ሊግ ማጠቃለያ ውድድር በአዲስ አበባ ከተማ ተካሂዷል።
በfinal ጨዋታው ብሔራዊ አልኮል የፌዴራል ማረሚያ ቤትን 3 ለ 0 በሆነ ሰፊ ውጤት በመርታት የዘንድሮው የውድድር ዘመን ሻምፒዮን መሆን ችሏል።
በሁለት ዙሮች ተከፍሎ የተከናወነው የዘንድሮው የሴቶች ፕሪሚየር ሊግ የመክፈቻው ዙር ውድድር በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ የተስተናገደ ሲሆን፣ ሁለተኛውና የማጠቃለያው ምዕራፍ ደግሞ በአዲስ አበባ ትንሻ ስታዲየም ፍጻሜውን አግኝቷል።
በዕለቱ በተከናወነው የሽልማት ሥነ-ሥርዓት ላይ በወጣት ስፖርተኞች ምልመላና በታዳጊዎች ዘርፍ ላሳየው ከፍተኛ ተሳትፎ የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ልዩ የዋንጫ ተሸላሚ ሆኗል።
በሌላ በኩል የፌዴራል ማረሚያ ቤቶች ክለብ ላለፉት 40 ዓመታት በኢትዮጵያ ስፖርት ውስጥ በተለይም ለቮሊቦል ስፖርት ዕድገትና መኖር ላበረከተው ዘመን ተሻጋሪ አስተዋጽኦ እንዲሁም ለ40ኛ ዓመት የምሥረታ በዓሉ መታሰቢያ የሚሆን ልዩ የክብር ዋንጫ ተበርክቶለታል።
የኢትዮጵያ ቮሊቦል ፌዴሬሽን የጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ተክሉ ሸዋዬ እንደገለጹት፣ ዘንድሮ ውድድሩ በበጀት እጥረት ምክንያት በአራት ክለቦች ብቻ የተገደበ ቢሆንም በታዩት ድንቅ ወጣት ተጫዋቾችና በነበረው ጠንካራ ፉክክር በጥሩ ጎኑ የሚገመገም ነው።
ኃላፊው አክለውም በቀጣይ ዓመት የወንዶችንና የሴቶችን ውድድር በአንድ ላይ በማቀናጀት ስፖርቱ የሚገባውን የመንግሥትና የባለድርሻ አካላት ትኩረት እንዲያገኝ ሰፊ የዝግጅት ሥራዎች እንደሚከናወኑ አስታውቀዋል።
#volleyball #sport #ethiopiansport #champions #womensvolleyball #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | የ2018 ዓ.ም የደራባ ሚድሮክ ሲሚንቶ የሴቶች ቮሊቦል ፕሪሚየር ሊግ ማጠቃለያ ውድድር በአዲስ አበባ ከተማ ተካሂዷል።
በfinal ጨዋታው ብሔራዊ አልኮል የፌዴራል ማረሚያ ቤትን 3 ለ 0 በሆነ ሰፊ ውጤት በመርታት የዘንድሮው የውድድር ዘመን ሻምፒዮን መሆን ችሏል።
በሁለት ዙሮች ተከፍሎ የተከናወነው የዘንድሮው የሴቶች ፕሪሚየር ሊግ የመክፈቻው ዙር ውድድር በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ የተስተናገደ ሲሆን፣ ሁለተኛውና የማጠቃለያው ምዕራፍ ደግሞ በአዲስ አበባ ትንሻ ስታዲየም ፍጻሜውን አግኝቷል።
በዕለቱ በተከናወነው የሽልማት ሥነ-ሥርዓት ላይ በወጣት ስፖርተኞች ምልመላና በታዳጊዎች ዘርፍ ላሳየው ከፍተኛ ተሳትፎ የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ልዩ የዋንጫ ተሸላሚ ሆኗል።
በሌላ በኩል የፌዴራል ማረሚያ ቤቶች ክለብ ላለፉት 40 ዓመታት በኢትዮጵያ ስፖርት ውስጥ በተለይም ለቮሊቦል ስፖርት ዕድገትና መኖር ላበረከተው ዘመን ተሻጋሪ አስተዋጽኦ እንዲሁም ለ40ኛ ዓመት የምሥረታ በዓሉ መታሰቢያ የሚሆን ልዩ የክብር ዋንጫ ተበርክቶለታል።
የኢትዮጵያ ቮሊቦል ፌዴሬሽን የጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ተክሉ ሸዋዬ እንደገለጹት፣ ዘንድሮ ውድድሩ በበጀት እጥረት ምክንያት በአራት ክለቦች ብቻ የተገደበ ቢሆንም በታዩት ድንቅ ወጣት ተጫዋቾችና በነበረው ጠንካራ ፉክክር በጥሩ ጎኑ የሚገመገም ነው።
ኃላፊው አክለውም በቀጣይ ዓመት የወንዶችንና የሴቶችን ውድድር በአንድ ላይ በማቀናጀት ስፖርቱ የሚገባውን የመንግሥትና የባለድርሻ አካላት ትኩረት እንዲያገኝ ሰፊ የዝግጅት ሥራዎች እንደሚከናወኑ አስታውቀዋል።
#volleyball #sport #ethiopiansport #champions #womensvolleyball #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
2 days ago
ኮካ ኮላ ኩባንያ የአለም ዋንጫን የመክፈቻ ስነስርአት በአዲስ አበባ በደመቀ ሁኔታ አከናወነ፡፡ የአለም ዋንጫ የረጅም ጊዜ አጋርና ዋና ስፖንሰር የሆነው ኮካ ኮላ ኩባንያ በመላው አለም የአለም ዋንጫ መክፈቻ ስነስርአትን በደመቀ ሁኔታ እንዲከናወን አድርጓል፡፡ ከእነዚህ ስነስርአቶች መካከል በአዲስ አበባ ከተማ ስካይ ላይት ሆቴል የተደረገው ዝግጅት አንዱ ነው፡፡ ትላንት ምሽት በተከናወነው በዚህ ዝግጅት በርካታ ታዋቂ ሰዎች፣ የኪነጥበብ ባለሙያዎች፣ የስፖርት ቤተሰቦችና ጋዜጠኞች የታደሙ ሲሆን ጋዜጠኛ ሰኢድ ኪያር ዝግጅቱን መርቶታል፡፡ በፕሮግራሙ ላይ የኮካ ኮላ ሲኒየር ማርኬቲንግ ማኔጀር ሜሮን ብርሀኑ ሲናገሩ ‹‹እግር ኳስ ከስፖርትነቱ ባለፈ ሰዎችን በስሜትና በፍቅር የሚያስተሳስር ሁለተንተናዊ ቋንቋ ነው›› ብለዋል፡፡ የ2026ቱ አለም ዋንጫ በታሪክ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው አገራትና ጨዋታዎች የሚስተናገዱበት መሆኑን ጠቁመውም፣ ኮካ ኮላ ትርጉም ባላቸው አቀራረቦች የኢትዮጵያን እግር ኳስ አፍቃሪዎች ከውድድሩ ደስታ ጋር ይበልጥ ለማቀራረብ ቁርጠኛ መሆኑን ገልፀዋል፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ የኮካኮላ ቢቨሬጅስ ተወካይ በበኩላቸው ኩባንያ በኢትዮጵያ ውስጥ ስላለው ጠንካራ ተሳትፎና ምርት ስርጭት ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡ በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ ውስጥ በአዲስ አበባ፣ ሰበታ፣ ባህር ዳርና ድሬደዋን ጨምሮ 5 ፋብሪካዎች እንዳሉት ጠቅሰውም በተለያየ መጠን በብርጭቶ ጠርሙስና በፕላስቲክ ማሸጊያዎች ምርቶቹን እያቀረበ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ኮካ ኮላ እ.ኤ.አ ከ1978 አንስቶ የፊፋ አለም ዋንጫ ይፋዊ ስፖንሰር መሆኑ የሚታወቅ ነው፡፡
3 days ago
የመጀመሪያው የኢትዮጵያ 10 ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ ሩጫ ውድድር በባህርዳር ከተማ ሊካሄድ ነው
#ethiopia | የመጀመሪያው የኢትዮጵያ 10 ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ ሩጫ ውድድር የፊታችን እሁድ ሰኔ 7 ቀን 2018 ዓ.ም በባህርዳር ከተማ በደመቀ ሁኔታ እንደሚካሄድ ተነገረ።
የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን በውድድሩ ቅድመ ዝግጅት ስራዎች ዙሪያ ለመገናኛ ብዙሃን በሰጠው መግለጫ፣ የፌዴሬሽኑ ከፍተኛ የቴክኒክ ባለሙያዎች ወደ ስፍራው በማቅናት አስፈላጊውን ዝግጅት እያከናወኑ እንደሚገኙ አስታውቋል።
ይህ የውድድር መድረክ በዋናነት አዳዲስ ተተኪ አትሌቶችን ለማፍራትና የውድድር እድሎችን ለመፍጠር ያለመ መሆኑም ተገልጿል።
በዚሁ የጎዳና ላይ ሩጫ ውድድር ላይ የግል ተሳታፊዎችን ጨምሮ ከ6 የተለያዩ ክለቦች የተውጣጡ 91 አትሌቶች እንደሚሳተፉ ታውቋል። በውድድሩ ከ1ኛ እስከ 8ኛ ያለውን ደረጃ ይዘው ለሚያጠናቅቁ አትሌቶችም የገንዘብ ሽልማት እንደሚበረከትላቸው ተገልጿል።
ይህንን ጋዜጣዊ መግለጫ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን የውድድርና ተሳትፎ ዳይሬክተር ተወካይ አቶ ጊዜ አድነው እና አቶ መሐሪ ነጋሽ በጋራ የሰጡት ሲሆን፣ ውድድሩ በአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን በቀጥታ ስርጭት ለተመልካች እንደሚተላለፍ ታውቋል።
#ethiopianathletics #bahirdar #streetrace #10krun #ethiopiansport #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | የመጀመሪያው የኢትዮጵያ 10 ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ ሩጫ ውድድር የፊታችን እሁድ ሰኔ 7 ቀን 2018 ዓ.ም በባህርዳር ከተማ በደመቀ ሁኔታ እንደሚካሄድ ተነገረ።
የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን በውድድሩ ቅድመ ዝግጅት ስራዎች ዙሪያ ለመገናኛ ብዙሃን በሰጠው መግለጫ፣ የፌዴሬሽኑ ከፍተኛ የቴክኒክ ባለሙያዎች ወደ ስፍራው በማቅናት አስፈላጊውን ዝግጅት እያከናወኑ እንደሚገኙ አስታውቋል።
ይህ የውድድር መድረክ በዋናነት አዳዲስ ተተኪ አትሌቶችን ለማፍራትና የውድድር እድሎችን ለመፍጠር ያለመ መሆኑም ተገልጿል።
በዚሁ የጎዳና ላይ ሩጫ ውድድር ላይ የግል ተሳታፊዎችን ጨምሮ ከ6 የተለያዩ ክለቦች የተውጣጡ 91 አትሌቶች እንደሚሳተፉ ታውቋል። በውድድሩ ከ1ኛ እስከ 8ኛ ያለውን ደረጃ ይዘው ለሚያጠናቅቁ አትሌቶችም የገንዘብ ሽልማት እንደሚበረከትላቸው ተገልጿል።
ይህንን ጋዜጣዊ መግለጫ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን የውድድርና ተሳትፎ ዳይሬክተር ተወካይ አቶ ጊዜ አድነው እና አቶ መሐሪ ነጋሽ በጋራ የሰጡት ሲሆን፣ ውድድሩ በአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን በቀጥታ ስርጭት ለተመልካች እንደሚተላለፍ ታውቋል።
#ethiopianathletics #bahirdar #streetrace #10krun #ethiopiansport #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
3 days ago
ታርጋ ለመቀየር የጊዜ ሰሌዳ ይወጣል‼️
ነባር ተሽከርካሪዎች አዲሱን ሰሌዳ የሚቀይሩት በሚወጣው የጊዜ ሰሌዳ መሠረት መሆኑ ተገለፀ።
የአዲስ አበባ ከተማ አሽከርካሪና ተሽከርካሪ ፈቃድና ቁጥጥር ባለስልጣን ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ዘገየ በላይነህ፣ አዲሱን የተሽከርካሪ ሰሌዳ አተገባበር አስመልክቶ ዛሬ መግለጫ ሰጥተዋል።
በመግለጫቸውም የአገልግሎት አሰጣጡን ሂደትና ለነባር ተሽከርካሪዎች የተዘጋጀውን አቅጣጫ ይፋ አድርገዋል።
በሥራ ላይ ያሉ ነባር ተሽከርካሪዎች አዲሱን ሰሌዳ የሚቀይሩት የትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ሚኒስቴር በሚያወጣው የጊዜ ሰሌዳ መሠረት መሆኑን ገልጸዋል።
አዲሱ ስማርት ሰሌዳ በአሁኑ ወቅት እየተሰጠ ያለው የተሸከርካሪ ታርጋ ለመዉሰድ ተመዝግበዉ በመጠባበቅ ላይ ላሉ እና ከዚህ በሁዋላ አዲስ ለሚመዘገቡ ተሽከርካሪዎች መሆኑን ገልጸዉ ፤ ተመዝግበው ሰሌዳ በመጠባበቅ ላይ ለሚገኙ ተገልጋዮች እንግልትና የጊዜ መባከን እንዳይኖር፣ ቀደም ሲል በተመዘገቡበት ቅደም-ተከተል መሠረት ከየቅርንጫፎቹ ጥሪ ሲደረግላቸዉ መጥተው አገልግሎቱን እንደሚወስዱ አቅጣጫ ሰጥተዋል።
#አዲሱ_ስማርት_ሰሌዳ
ከተሽከርካሪው ዕድሜ ጋር እኩል የሚዘልቅ (Durability)፦ ሰሌዳው ጠንካራና የረጅም ጊዜ አገልግሎት የሚሰጥ በመሆኑ፣ ተሽከርካሪው የአገልግሎት ለውጥ በሚያደርግበት ጊዜ የማይቀየርና ተጨማሪ ወጪን ሙሉ በሙሉ የሚያስቀር ነው።
ከፍተኛ የደህንነት ጥንቃቄ የተደረገበት በመሆኑ ማጭበርበር ይከላከላል።
ሰሌዳው ዘመናዊ ቺፕና የፊት መስታወት ላይ የሚለጠፍ የRFID መለያ አብሮት ያለው በመሆኑ፣ የተሽከርካሪውን አሁናዊ መረጃ (Real-time data) በሰከንዶች ውስጥ ለማወቅ ያስችላል።
ሰሌዳዉ በቪየና ኮንቬንሽን መሠረት ለሀገራችን የተሰጠውን ዓለም አቀፍ የ "ETH" ኮድ ይዟል።
ነባር ተሽከርካሪዎች አዲሱን ሰሌዳ የሚቀይሩት በሚወጣው የጊዜ ሰሌዳ መሠረት መሆኑ ተገለፀ።
የአዲስ አበባ ከተማ አሽከርካሪና ተሽከርካሪ ፈቃድና ቁጥጥር ባለስልጣን ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ዘገየ በላይነህ፣ አዲሱን የተሽከርካሪ ሰሌዳ አተገባበር አስመልክቶ ዛሬ መግለጫ ሰጥተዋል።
በመግለጫቸውም የአገልግሎት አሰጣጡን ሂደትና ለነባር ተሽከርካሪዎች የተዘጋጀውን አቅጣጫ ይፋ አድርገዋል።
በሥራ ላይ ያሉ ነባር ተሽከርካሪዎች አዲሱን ሰሌዳ የሚቀይሩት የትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ሚኒስቴር በሚያወጣው የጊዜ ሰሌዳ መሠረት መሆኑን ገልጸዋል።
አዲሱ ስማርት ሰሌዳ በአሁኑ ወቅት እየተሰጠ ያለው የተሸከርካሪ ታርጋ ለመዉሰድ ተመዝግበዉ በመጠባበቅ ላይ ላሉ እና ከዚህ በሁዋላ አዲስ ለሚመዘገቡ ተሽከርካሪዎች መሆኑን ገልጸዉ ፤ ተመዝግበው ሰሌዳ በመጠባበቅ ላይ ለሚገኙ ተገልጋዮች እንግልትና የጊዜ መባከን እንዳይኖር፣ ቀደም ሲል በተመዘገቡበት ቅደም-ተከተል መሠረት ከየቅርንጫፎቹ ጥሪ ሲደረግላቸዉ መጥተው አገልግሎቱን እንደሚወስዱ አቅጣጫ ሰጥተዋል።
#አዲሱ_ስማርት_ሰሌዳ
ከተሽከርካሪው ዕድሜ ጋር እኩል የሚዘልቅ (Durability)፦ ሰሌዳው ጠንካራና የረጅም ጊዜ አገልግሎት የሚሰጥ በመሆኑ፣ ተሽከርካሪው የአገልግሎት ለውጥ በሚያደርግበት ጊዜ የማይቀየርና ተጨማሪ ወጪን ሙሉ በሙሉ የሚያስቀር ነው።
ከፍተኛ የደህንነት ጥንቃቄ የተደረገበት በመሆኑ ማጭበርበር ይከላከላል።
ሰሌዳው ዘመናዊ ቺፕና የፊት መስታወት ላይ የሚለጠፍ የRFID መለያ አብሮት ያለው በመሆኑ፣ የተሽከርካሪውን አሁናዊ መረጃ (Real-time data) በሰከንዶች ውስጥ ለማወቅ ያስችላል።
ሰሌዳዉ በቪየና ኮንቬንሽን መሠረት ለሀገራችን የተሰጠውን ዓለም አቀፍ የ "ETH" ኮድ ይዟል።
Sponsored by
Surafel
3 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የኢትዮጵያ መንግስት ለ2026/27 በጀት ዓመት ካቀረበው 2.34 ትሪሊዮን ብር ሪከርድ በጀት ውስጥ፣ 542.1 ቢሊዮን ብር (ወይም 3.4 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር) ለዕዳ ክፍያ ማዋሉ ተገለጸ። ይህ ግዙፍ ምደባ መንግስት ላቀደው ጠቅላላ በጀት የዕዳ መክፈያ ግዴታዎች ምን ያህል ከፍተኛውን የወጪ ድርሻ እየወሰዱ እንደሆነ በግልጽ የሚያሳይ ነው። የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሺዴ በጀቱን ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ያቀረቡ ሲሆን የበጀት ማዕቀፉ ከዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም (IMF) ጋር የሚደረገውን የኢኮኖሚ ማሻሻያ፣ የውጭ ምንዛሬ ገበያውን ከፊል ነጻ ማድረግን፣ የ10.1 በመቶ የኢኮኖሚ ዕድገት ግብን እና እያደገ የመጣውን የወጪ ፍላጎት ታሳቢ ያደረገ መሆኑ ተገልጿል።
በአሁኑ ወቅት የዕዳ ክፍያ በመንግስት በጀት ውስጥ እጅግ ከፍተኛውን ድርሻ ይዟል። ይህ የዕዳ ክፍያ ከመደበኛ ወጪው 43.8 በመቶውን የሚሸፍን ነው። ይሁን እንጂ ትክክለኛው የዕዳ መክፈያ ፍላጎት 581.1 ቢሊዮን ብር መሆኑን ባለስልጣናቱ የገለጹ ሲሆን፣ ይህም የ39 ቢሊዮን ብር የፋይናንስ ክፍተት ፈጥሯል። ለዕዳ ክፍያ የተመደበው የዘንድሮው በጀት፣ ባለፈው በጀት ዓመት (2025/26) ተመድቦ ከነበረው 463.4 ቢሊዮን ብር ጋር ሲነጻጸር ከፍተኛ ጭማሪ አሳይቷል። የዚህ ጭማሪ ዋና ምክንያቶች ኢትዮጵያ ያለባት ከባድ የብድር ጫና እንዲሁም የብር የመግዛት አቅም መዳከም (በብር የሚከፈለውን የውጭ ዕዳ መጠን ስለሚያሳድገው) ናቸው። ኢትዮጵያ በ2023 መገባደጃ ላይ የአንድ ቢሊዮን ዶላር ዩሮቦንድ ዕዳዋን መክፈል ተስኗት የነበረ ሲሆን፣ የዕዳ ማክበጃ ድርድር በማድረግ ላይ ትገኛለች።
በገቢ እና ወጪ ዝርዝር ዕቅዱ መሰረት፣ መንግስት 1.82 ትሪሊዮን ብር ገቢ እና እርዳታ ለመሰብሰብ ያቀደ ሲሆን፣ ከዚህ ውስጥ 1.5 ትሪሊዮን ብሩ (ወይም 82 በመቶው) ከታክስ የሚሰበሰብ ነው። የታክስ አሰባሰቡን በዝርዝር ስንመለከት፣ ከደመወዝ ገቢ ግብር 97.3 ቢሊዮን ብር፣ ከሀገር ውስጥ ቀጥታ ታክስ 427.5 ቢሊዮን ብር፣ ከንግድ ትርፍ ግብር 263 ቢሊዮን ብር፣ ከተዘዋዋሪ ታክስ 278 ቢሊዮን ብር፣ እንዲሁም ከተጨማሪ እሴት ታክስ (VAT) 339 ቢሊዮን ብር ይሰበሰባል ተብሎ ይጠበቃል።
በሌላ በኩል 1.2 ትሪሊዮን ብር ለመደበኛ ወጪ እንዲሁም 568 ቢሊዮን ብር ለካፒታል ወጪ ተመድቧል። ከዚህም በተጨማሪ ለማዳበሪያ፣ ለነዳጅ እና ለኢትዮጵያ ነዳጅ ድርጅት አቅም ማሳደጊያ የሚውል 236.4 ቢሊዮን ብር የድጎማ በጀት ተይዟል። ለፌዴራል እና ለክልል አስተዳደሮች 520.6 ቢሊዮን ብር የበጀት ድጋፍ ሲመደብ፣ 14 ቢሊዮን ብር ደግሞ ለዘላቂ ልማት ግቦች ማስፈጸሚያ እንዲውል ተወስኗል።
መንግስት ወጪውን ቢያሳድግም የ308.6 ቢሊዮን ብር (የጠቅላላ የሀገር ውስጥ ምርት 1.4 በመቶ) የተጣራ የበጀት ጉድለት ያጋጥመዋል ተብሎ ተገምቷል። ይህንን ክፍተት ለመሸፈን መንግስት በአብዛኛው ከሀገር ውስጥ በሚያገኘው 302.9 ቢሊዮን ብር ብድር ላይ የሚመረኮዝ ሲሆን፣ ከውጭ ምንጮች ይጠበቃል የተባለው 5.7 ቢሊዮን ብር ብቻ ነው። ይህ ሁኔታ የውጭ ፋይናንስ ውስን በመሆኑ መንግስት ክፍተቱን ለመድፈን በሀገር ውስጥ ብድር ላይ በእጅጉ ጥገኛ መሆኑን ያሳያል።
በጀቱ በሚኒስትሮች ምክር ቤት ጸድቆ ለፓርላማ የተመራ ሲሆን የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት መንግስት የዕድገት ፍላጎቱን፣ እያሻቀበ ከመጣው የዕዳ ክፍያ፣ የድጎማ ጫና እና ውስን ከሆነው የውጭ ፋይናንስ ጋር እንዴት አጣጥሞ እንደሚሄድ በበጀቱ ላይ ሰፋ ያለ ውይይት ያደርጋሉ ተብሎ ይጠበቃል።
በአሁኑ ወቅት የዕዳ ክፍያ በመንግስት በጀት ውስጥ እጅግ ከፍተኛውን ድርሻ ይዟል። ይህ የዕዳ ክፍያ ከመደበኛ ወጪው 43.8 በመቶውን የሚሸፍን ነው። ይሁን እንጂ ትክክለኛው የዕዳ መክፈያ ፍላጎት 581.1 ቢሊዮን ብር መሆኑን ባለስልጣናቱ የገለጹ ሲሆን፣ ይህም የ39 ቢሊዮን ብር የፋይናንስ ክፍተት ፈጥሯል። ለዕዳ ክፍያ የተመደበው የዘንድሮው በጀት፣ ባለፈው በጀት ዓመት (2025/26) ተመድቦ ከነበረው 463.4 ቢሊዮን ብር ጋር ሲነጻጸር ከፍተኛ ጭማሪ አሳይቷል። የዚህ ጭማሪ ዋና ምክንያቶች ኢትዮጵያ ያለባት ከባድ የብድር ጫና እንዲሁም የብር የመግዛት አቅም መዳከም (በብር የሚከፈለውን የውጭ ዕዳ መጠን ስለሚያሳድገው) ናቸው። ኢትዮጵያ በ2023 መገባደጃ ላይ የአንድ ቢሊዮን ዶላር ዩሮቦንድ ዕዳዋን መክፈል ተስኗት የነበረ ሲሆን፣ የዕዳ ማክበጃ ድርድር በማድረግ ላይ ትገኛለች።
በገቢ እና ወጪ ዝርዝር ዕቅዱ መሰረት፣ መንግስት 1.82 ትሪሊዮን ብር ገቢ እና እርዳታ ለመሰብሰብ ያቀደ ሲሆን፣ ከዚህ ውስጥ 1.5 ትሪሊዮን ብሩ (ወይም 82 በመቶው) ከታክስ የሚሰበሰብ ነው። የታክስ አሰባሰቡን በዝርዝር ስንመለከት፣ ከደመወዝ ገቢ ግብር 97.3 ቢሊዮን ብር፣ ከሀገር ውስጥ ቀጥታ ታክስ 427.5 ቢሊዮን ብር፣ ከንግድ ትርፍ ግብር 263 ቢሊዮን ብር፣ ከተዘዋዋሪ ታክስ 278 ቢሊዮን ብር፣ እንዲሁም ከተጨማሪ እሴት ታክስ (VAT) 339 ቢሊዮን ብር ይሰበሰባል ተብሎ ይጠበቃል።
በሌላ በኩል 1.2 ትሪሊዮን ብር ለመደበኛ ወጪ እንዲሁም 568 ቢሊዮን ብር ለካፒታል ወጪ ተመድቧል። ከዚህም በተጨማሪ ለማዳበሪያ፣ ለነዳጅ እና ለኢትዮጵያ ነዳጅ ድርጅት አቅም ማሳደጊያ የሚውል 236.4 ቢሊዮን ብር የድጎማ በጀት ተይዟል። ለፌዴራል እና ለክልል አስተዳደሮች 520.6 ቢሊዮን ብር የበጀት ድጋፍ ሲመደብ፣ 14 ቢሊዮን ብር ደግሞ ለዘላቂ ልማት ግቦች ማስፈጸሚያ እንዲውል ተወስኗል።
መንግስት ወጪውን ቢያሳድግም የ308.6 ቢሊዮን ብር (የጠቅላላ የሀገር ውስጥ ምርት 1.4 በመቶ) የተጣራ የበጀት ጉድለት ያጋጥመዋል ተብሎ ተገምቷል። ይህንን ክፍተት ለመሸፈን መንግስት በአብዛኛው ከሀገር ውስጥ በሚያገኘው 302.9 ቢሊዮን ብር ብድር ላይ የሚመረኮዝ ሲሆን፣ ከውጭ ምንጮች ይጠበቃል የተባለው 5.7 ቢሊዮን ብር ብቻ ነው። ይህ ሁኔታ የውጭ ፋይናንስ ውስን በመሆኑ መንግስት ክፍተቱን ለመድፈን በሀገር ውስጥ ብድር ላይ በእጅጉ ጥገኛ መሆኑን ያሳያል።
በጀቱ በሚኒስትሮች ምክር ቤት ጸድቆ ለፓርላማ የተመራ ሲሆን የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት መንግስት የዕድገት ፍላጎቱን፣ እያሻቀበ ከመጣው የዕዳ ክፍያ፣ የድጎማ ጫና እና ውስን ከሆነው የውጭ ፋይናንስ ጋር እንዴት አጣጥሞ እንደሚሄድ በበጀቱ ላይ ሰፋ ያለ ውይይት ያደርጋሉ ተብሎ ይጠበቃል።
3 days ago
⚠️ሰበር - ባለሃብቱ አቶ ወርቁ አይተነው በኖርዌይ በቲክቶከሯ ሄለን ደሳለኝ አራዶ (Helen Desalegn Arado) ላይ ፈጣን እና አስተማሪ ህጋዊ እርምጃ ወሰዱ #ethiopia #justice #accountability #lawandorder #workuaytenew #helendesalegnarado
3 days ago
የተፈጥሮ ድንቅ ውበት በልኩ የተገለጠበት ሥፍራ… ወንጪ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 4፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የገበታ ለሀገር ፕሮጀክት አካል የሆነው ወንጪ ደንዲ ኢኮ ቱሪዝም መንደር እና ሎጅ የተፈጥሮ ድንቅ ውበት በሚገርም ሁኔታ የተገለጠበት ሥፍራ ነው፡፡
የኦሮሚያ ክልል ቱሪዝም ኮሚሽን ም/ኮሚሽነር ነጋ ወዳጆ ፥ ወንጪ ተፈጥሮ፣ ታሪክ፣ ቅርስ እና ባህል በአንድ ተሰናስለው የሚገኙበት ድንቅ የቱሪስት መዳረሻ ነው ይላሉ፡፡
የአካባቢውን መልክዓ ምድር፣ የአኗኗር ዘዬ፣ ባህል እና ማንነት በማስተሳሰር ለሌሎች የቱሪስት መዳረሻዎች ምሳሌ በሚሆን መልኩ መገንባቱን አውስተዋል፡፡
ማራኪ ተፈጥሮ የሚስተዋልበትን ወንጪ ደንዲ ኢኮ ቱሪዝም መንደር እና ሎጅ የቱሪስት ማዕከል ለማድረግ በትኩረት መሰራቱን ተናግረዋል፡፡
በተለይም ለቱሪስቶች አስፈላጊ የሆኑ መሰረተ ልማቶችን ከማሟላት አንጻር በትብብር የተከናወነው ሥራ ውጤታማ መሆኑን አንስተዋል፡፡
በዚህ መሰረትም በቱሪስት መዳረሻው የትራንስፖርት፣ የማረፊያ ክፍሎች እና ሌሎች አገልግሎቶች መዘጋጀታቸውን አመልክተዋል፡፡
በመንደሩ የልማት ተነሺዎች ለመቋቋሚያ የተሰሩላቸውን ደረጃቸውን የጠበቁ ቪላ ቤቶች ለጎብኚዎች በተመጣጣኝ ዋጋ እያከራዩ ገቢ ያገኛሉ ነው ያሉት፡፡
ይህም የቱሪስቶችን ቆይታ ከማራዘም ባለፈ ጎብኚዎች አካባቢውን በደንብ ተመልክተው አይረሴ ጊዜን እንዲያሳልፉ ጉልህ ሚና እየተጫወተ መሆኑን አቶ ነጋ ለፋና ዲጂታል ተናግረዋል፡፡
በተጨማሪም የአካባቢውን ባህላዊ ምግቦች፣ ማር፣ የቡና አፈላል ሥርዓት እና ሌሎች ባህላዊ ክዋኔዎችን ለጎብኚዎች በማቅረብ ተጠቃሚ መሆናቸውን አብራርተዋል፡፡
አሁን ላይም በርካታ የሀገር ውስጥና የውጭ ሀገራት ቱሪስቶች ወንጪ ደንዲ ኢኮ ቱሪዝም መንደርን እየጎበኙ እንደሚገኙ ነው የገለጹት፡፡
የሀገር ውስጥና የውጭ ቱሪስቶች የወንጪ ደንዲ ኢኮ ቱሪዝም መንደርን በመጎብኘት አይረሴ ጊዜ እንዲያሳልፉም ጥሪ አቅርበዋል።
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 4፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የገበታ ለሀገር ፕሮጀክት አካል የሆነው ወንጪ ደንዲ ኢኮ ቱሪዝም መንደር እና ሎጅ የተፈጥሮ ድንቅ ውበት በሚገርም ሁኔታ የተገለጠበት ሥፍራ ነው፡፡
የኦሮሚያ ክልል ቱሪዝም ኮሚሽን ም/ኮሚሽነር ነጋ ወዳጆ ፥ ወንጪ ተፈጥሮ፣ ታሪክ፣ ቅርስ እና ባህል በአንድ ተሰናስለው የሚገኙበት ድንቅ የቱሪስት መዳረሻ ነው ይላሉ፡፡
የአካባቢውን መልክዓ ምድር፣ የአኗኗር ዘዬ፣ ባህል እና ማንነት በማስተሳሰር ለሌሎች የቱሪስት መዳረሻዎች ምሳሌ በሚሆን መልኩ መገንባቱን አውስተዋል፡፡
ማራኪ ተፈጥሮ የሚስተዋልበትን ወንጪ ደንዲ ኢኮ ቱሪዝም መንደር እና ሎጅ የቱሪስት ማዕከል ለማድረግ በትኩረት መሰራቱን ተናግረዋል፡፡
በተለይም ለቱሪስቶች አስፈላጊ የሆኑ መሰረተ ልማቶችን ከማሟላት አንጻር በትብብር የተከናወነው ሥራ ውጤታማ መሆኑን አንስተዋል፡፡
በዚህ መሰረትም በቱሪስት መዳረሻው የትራንስፖርት፣ የማረፊያ ክፍሎች እና ሌሎች አገልግሎቶች መዘጋጀታቸውን አመልክተዋል፡፡
በመንደሩ የልማት ተነሺዎች ለመቋቋሚያ የተሰሩላቸውን ደረጃቸውን የጠበቁ ቪላ ቤቶች ለጎብኚዎች በተመጣጣኝ ዋጋ እያከራዩ ገቢ ያገኛሉ ነው ያሉት፡፡
ይህም የቱሪስቶችን ቆይታ ከማራዘም ባለፈ ጎብኚዎች አካባቢውን በደንብ ተመልክተው አይረሴ ጊዜን እንዲያሳልፉ ጉልህ ሚና እየተጫወተ መሆኑን አቶ ነጋ ለፋና ዲጂታል ተናግረዋል፡፡
በተጨማሪም የአካባቢውን ባህላዊ ምግቦች፣ ማር፣ የቡና አፈላል ሥርዓት እና ሌሎች ባህላዊ ክዋኔዎችን ለጎብኚዎች በማቅረብ ተጠቃሚ መሆናቸውን አብራርተዋል፡፡
አሁን ላይም በርካታ የሀገር ውስጥና የውጭ ሀገራት ቱሪስቶች ወንጪ ደንዲ ኢኮ ቱሪዝም መንደርን እየጎበኙ እንደሚገኙ ነው የገለጹት፡፡
የሀገር ውስጥና የውጭ ቱሪስቶች የወንጪ ደንዲ ኢኮ ቱሪዝም መንደርን በመጎብኘት አይረሴ ጊዜ እንዲያሳልፉም ጥሪ አቅርበዋል።
3 days ago
በ"ቪቫ ሶፍት" የንግድ ምልክት መብት ጥሰት የተጠረጠሩት ግለሰብ ላይ ፍርድ ቤቱ ተጨማሪ የ7 ቀናት የምርመራ ጊዜ ፈቀደ፤
በ"ቪቫ ሶፍት" ምርት ላይ ተፈጽሟል በተባለ የንግድ ምልክት መብት ጥሰት ወንጀል ተጠርጥረው በቁጥጥር ስር የዋሉት አቶ ሰይድ መሐመድኑር ዑመር ላይ የፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ 1ኛ የጊዜ ቀጠሮ ወንጀል ችሎት ዛሬ ሰኔ 4 ቀን 2018 ዓ.ም በዋለው ችሎት ተጨማሪ የ7 ቀናት የምርመራ ማጣሪያ ጊዜ ፈቅዷል።
ፍርድ ቤቱ ቀደም ሲል በግንቦት 26 ቀን 2018 ዓ.ም በዋለው ችሎት ለፖሊስ የ7 ቀናት የምርመራ ማጣሪያ ጊዜ ፈቅዶ ለዛሬ ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቶ የነበረ ሲሆን፣ ዛሬ በዋለው ችሎት የፌዴራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ቢሮ እስካሁን ያከናወናቸውን ተግባራትና የቀሩትን የምርመራ ሂደቶች ለችሎቱ አቅርቧል።
ፖሊስ ለፍርድ ቤቱ ባቀረበው ማብራሪያ፣ ድርጊቱ "ፒዩር ዉድ ፐልፕ ኤንድ ፔፐር ፓኬጂንግ" ኃላ/የተ/የግ/ማህበር በኢትዮጵያ አዕምሯዊ ንብረት ባለስልጣን ሕጋዊ የምዝገባ ሰርተፍኬት ቁጥር LTM/3249/2017 የተሰጠውንና በዓለም አቀፍ ምድብ 16 ሥር የሚገኘውን የ"VIVa" (ቪቫ ሶፍት) የንግድ ምልክት ያለ ባለቤቱ ዕውቅና መጠቀምን የሚመለከት መሆኑን አስታውሷል። ተጠርጣሪው ከ2016 ዓ.ም ጀምሮ የቪቫ ሶፍትን ማሸጊያ ፕላስቲክ ሕገ-ወጥ በሆነ መንገድ አመሳስለው በመሥራት፣ ጥራቱን ያልጠበቀ፣ ፎርጅድ የሶፍት ምርት በአዲስ አበባና በተለያዩ ክልሎች በድብቅ ሲያሰራጩ እንደነበር በመግለጽ፣ ድርጊቱ ሸማቹን የማታለል፣ ጤናማ የገበያ ውድድርን የማዛባትና በመንግስት ታክስ እንዲሁም በኢኮኖሚው ላይ ቀውስ ለመፍጠር ሆን ተብሎ የተፈጸመ ውስብስብ ወንጀል መሆኑን በድጋሚ አስረድቷል።
ባለፉት ቀናት ውስጥ የ4 ሰዎችን ምስክርነት መቀበሉን ያመለከተው ፖሊስ፣ ለኢትዮጵያ አዕምሯዊ ንብረት ባለስልጣን፣ ለኢትዮጵያ ተስማሚነት ምዘና ድርጅት፣ ለኢትዮጵያ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት፣ ለኦሮሚያ ገቢዎች ቢሮ፣ ለኦሮሚያ ንግድ ቢሮና ለሌሎች ጉዳዩ ለሚመለከታቸው ተቋማት ወንጀሉን ሊያስረዱ የሚችሉ መረጃዎች እንዲሰጡት ጠይቆ ውጤቱን በመጠባበቅ ላይ እንደሚገኝ ገልጿል።
በተጨማሪም ከኢትዮጵያ አዕምሯዊ ንብረት ባለስልጣን እና ከኢትዮጵያ ተስማሚነት ምዘና ድርጅት የባለሙያ አስተያየት ወይም ምስክርነት መቀበል እንደሚቀረው እንዲሁም በክልል መጋዘን ውስጥ ተከማችቶ የሚገኝ ፎርጅድ የሶፍት ምርትን ለመመርመር ጊዜ እንደሚያስፈልገው ፖሊስ አስረድቷል። ተጠርጣሪው በዋስትና ቢወጡ ከባለሙያዎቹ የሚሰጡ ምስክርነቶችን ሊያስቱና ገና ካልተያዙ ግብረአበሮቻቸው ጋር በመሆንም የምርመራ ሥራውን ሊያደናቅፉ ስለሚችሉ፣ የምርመራ መዝገቡን በባለሙያዎች ምስክርነት እና በሰነድ አሟልቶ ለመጨረስ የ14 ቀን ተጨማሪ የምርመራ ማጣሪያ ጊዜ እንዲሰጠው ጠይቋል።
የግራ ቀኙን ክርክር የመረመረው የፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ 1ኛ የጊዜ ቀጠሮ ወንጀል ችሎት፣ የፖሊስን ጥያቄ መርምሮ የ7 ቀናት የምርመራ ማጣሪያ ጊዜ የፈቀደ ሲሆን፣ በቀጣይ የምርመራ ውጤቱን ለመጨረሻ ጊዜ ለመስማት ለሰኔ 11 ቀን 2018 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል።
በ"ቪቫ ሶፍት" ምርት ላይ ተፈጽሟል በተባለ የንግድ ምልክት መብት ጥሰት ወንጀል ተጠርጥረው በቁጥጥር ስር የዋሉት አቶ ሰይድ መሐመድኑር ዑመር ላይ የፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ 1ኛ የጊዜ ቀጠሮ ወንጀል ችሎት ዛሬ ሰኔ 4 ቀን 2018 ዓ.ም በዋለው ችሎት ተጨማሪ የ7 ቀናት የምርመራ ማጣሪያ ጊዜ ፈቅዷል።
ፍርድ ቤቱ ቀደም ሲል በግንቦት 26 ቀን 2018 ዓ.ም በዋለው ችሎት ለፖሊስ የ7 ቀናት የምርመራ ማጣሪያ ጊዜ ፈቅዶ ለዛሬ ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቶ የነበረ ሲሆን፣ ዛሬ በዋለው ችሎት የፌዴራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ቢሮ እስካሁን ያከናወናቸውን ተግባራትና የቀሩትን የምርመራ ሂደቶች ለችሎቱ አቅርቧል።
ፖሊስ ለፍርድ ቤቱ ባቀረበው ማብራሪያ፣ ድርጊቱ "ፒዩር ዉድ ፐልፕ ኤንድ ፔፐር ፓኬጂንግ" ኃላ/የተ/የግ/ማህበር በኢትዮጵያ አዕምሯዊ ንብረት ባለስልጣን ሕጋዊ የምዝገባ ሰርተፍኬት ቁጥር LTM/3249/2017 የተሰጠውንና በዓለም አቀፍ ምድብ 16 ሥር የሚገኘውን የ"VIVa" (ቪቫ ሶፍት) የንግድ ምልክት ያለ ባለቤቱ ዕውቅና መጠቀምን የሚመለከት መሆኑን አስታውሷል። ተጠርጣሪው ከ2016 ዓ.ም ጀምሮ የቪቫ ሶፍትን ማሸጊያ ፕላስቲክ ሕገ-ወጥ በሆነ መንገድ አመሳስለው በመሥራት፣ ጥራቱን ያልጠበቀ፣ ፎርጅድ የሶፍት ምርት በአዲስ አበባና በተለያዩ ክልሎች በድብቅ ሲያሰራጩ እንደነበር በመግለጽ፣ ድርጊቱ ሸማቹን የማታለል፣ ጤናማ የገበያ ውድድርን የማዛባትና በመንግስት ታክስ እንዲሁም በኢኮኖሚው ላይ ቀውስ ለመፍጠር ሆን ተብሎ የተፈጸመ ውስብስብ ወንጀል መሆኑን በድጋሚ አስረድቷል።
ባለፉት ቀናት ውስጥ የ4 ሰዎችን ምስክርነት መቀበሉን ያመለከተው ፖሊስ፣ ለኢትዮጵያ አዕምሯዊ ንብረት ባለስልጣን፣ ለኢትዮጵያ ተስማሚነት ምዘና ድርጅት፣ ለኢትዮጵያ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት፣ ለኦሮሚያ ገቢዎች ቢሮ፣ ለኦሮሚያ ንግድ ቢሮና ለሌሎች ጉዳዩ ለሚመለከታቸው ተቋማት ወንጀሉን ሊያስረዱ የሚችሉ መረጃዎች እንዲሰጡት ጠይቆ ውጤቱን በመጠባበቅ ላይ እንደሚገኝ ገልጿል።
በተጨማሪም ከኢትዮጵያ አዕምሯዊ ንብረት ባለስልጣን እና ከኢትዮጵያ ተስማሚነት ምዘና ድርጅት የባለሙያ አስተያየት ወይም ምስክርነት መቀበል እንደሚቀረው እንዲሁም በክልል መጋዘን ውስጥ ተከማችቶ የሚገኝ ፎርጅድ የሶፍት ምርትን ለመመርመር ጊዜ እንደሚያስፈልገው ፖሊስ አስረድቷል። ተጠርጣሪው በዋስትና ቢወጡ ከባለሙያዎቹ የሚሰጡ ምስክርነቶችን ሊያስቱና ገና ካልተያዙ ግብረአበሮቻቸው ጋር በመሆንም የምርመራ ሥራውን ሊያደናቅፉ ስለሚችሉ፣ የምርመራ መዝገቡን በባለሙያዎች ምስክርነት እና በሰነድ አሟልቶ ለመጨረስ የ14 ቀን ተጨማሪ የምርመራ ማጣሪያ ጊዜ እንዲሰጠው ጠይቋል።
የግራ ቀኙን ክርክር የመረመረው የፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ 1ኛ የጊዜ ቀጠሮ ወንጀል ችሎት፣ የፖሊስን ጥያቄ መርምሮ የ7 ቀናት የምርመራ ማጣሪያ ጊዜ የፈቀደ ሲሆን፣ በቀጣይ የምርመራ ውጤቱን ለመጨረሻ ጊዜ ለመስማት ለሰኔ 11 ቀን 2018 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል።
Sponsored by
Surafel
3 days ago
አዲሱ የተሽከርካሪ ሰሌዳ በአዲስ አበባ ከተማ መሰጠት ተጀመረ
#ethiopia | ETH የሚል ዓለም አቀፋዊ ኮድ የያዘዉ አዲሱ ሰሌዳ በአዲስ አበባ ሰሌዳ ለመዉሰድ ተመዝግበው እየተጠባበቁ ባሉ አዲስ ተሽከርካሪዎች ላይ ከሰኔ 4 ጀምሮ ተግባራዊ መደረግ መጀመሩ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የአሽከርካሪ እና ተሽከርካሪ ቁጥጥር ባለስልጣን አስታውቋል ።
የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ዘገየ በላይነህ አዲሱ ሰሌዳ ሀገራዊ ይዘት ያለዉ ፣ ፎርጂድ የማይሰራ ፣የሀብት ብክነትን የሚቀነስ ፣ለህግ ማስከበር የሚመች ፣ስርቆትንና ህገወጥ ዝዉዉርን ለመከላከል የሚረዳ መሆኑን መናገራቸዉን ብስራት ሬዲዮ ሠምቷል።
የመጀመሪያዉ ሰሌዳ ባለስልጣኑ ካሉት 11 ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤቶች አንዱ በሆነዉ የየካ ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት መሰጠቱ ተገልጿል ።
በብዙሃን ትራንስፓርት እና የግል ተሽከርካሪዎች የሰሌዳ ዋጋዉ ላይ ልዩነት እንደሚኖረዉ በትራንስፖርትና ሎጂስቲክ ሚኒስቴር የትራንስፖርት አገልግሎት ዘርፍ ቁጥጥር አማካሪ አቶ አሰፋ ሀዲስ ተናግረዋል ።
አዲሱ ሰሌዳ ተሽከርካሪዉ እስኪወገድ ድረስ የሚያገለግል መሆኑን የገለፀዉ ባለስልጣኑ ከ800 ሺህ በላይ ተሽከርካሪዎች መኖራቸዉንና ሰሌዳዉ ተወስዶ መቼ ይጠናቀቃል የሚለዉ በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የሚወሰን መሆኑን ገልጿል ።
በአዲስ አበባ ከተማ የተወሰነ ከተሄደበት በኃላ በክልሎችም የትራንስፖርት እና ሎጀስቲክ ሚኒስቴር በሚያስቀምጣቸው የጊዜ እቅድ ሰሌዳዉን የመቀየር ሂደቱ እንደሚተገበር ተገልጿል ያለው ብስራት ኤፍ ኤም ነው።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#ethiopia | ETH የሚል ዓለም አቀፋዊ ኮድ የያዘዉ አዲሱ ሰሌዳ በአዲስ አበባ ሰሌዳ ለመዉሰድ ተመዝግበው እየተጠባበቁ ባሉ አዲስ ተሽከርካሪዎች ላይ ከሰኔ 4 ጀምሮ ተግባራዊ መደረግ መጀመሩ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የአሽከርካሪ እና ተሽከርካሪ ቁጥጥር ባለስልጣን አስታውቋል ።
የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ዘገየ በላይነህ አዲሱ ሰሌዳ ሀገራዊ ይዘት ያለዉ ፣ ፎርጂድ የማይሰራ ፣የሀብት ብክነትን የሚቀነስ ፣ለህግ ማስከበር የሚመች ፣ስርቆትንና ህገወጥ ዝዉዉርን ለመከላከል የሚረዳ መሆኑን መናገራቸዉን ብስራት ሬዲዮ ሠምቷል።
የመጀመሪያዉ ሰሌዳ ባለስልጣኑ ካሉት 11 ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤቶች አንዱ በሆነዉ የየካ ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት መሰጠቱ ተገልጿል ።
በብዙሃን ትራንስፓርት እና የግል ተሽከርካሪዎች የሰሌዳ ዋጋዉ ላይ ልዩነት እንደሚኖረዉ በትራንስፖርትና ሎጂስቲክ ሚኒስቴር የትራንስፖርት አገልግሎት ዘርፍ ቁጥጥር አማካሪ አቶ አሰፋ ሀዲስ ተናግረዋል ።
አዲሱ ሰሌዳ ተሽከርካሪዉ እስኪወገድ ድረስ የሚያገለግል መሆኑን የገለፀዉ ባለስልጣኑ ከ800 ሺህ በላይ ተሽከርካሪዎች መኖራቸዉንና ሰሌዳዉ ተወስዶ መቼ ይጠናቀቃል የሚለዉ በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የሚወሰን መሆኑን ገልጿል ።
በአዲስ አበባ ከተማ የተወሰነ ከተሄደበት በኃላ በክልሎችም የትራንስፖርት እና ሎጀስቲክ ሚኒስቴር በሚያስቀምጣቸው የጊዜ እቅድ ሰሌዳዉን የመቀየር ሂደቱ እንደሚተገበር ተገልጿል ያለው ብስራት ኤፍ ኤም ነው።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
3 days ago
የነዋሪዎች መረጃን ማዘመን ለቀልጣፋ አገልግሎትና ለነገዋ ዲጂታል ኢትዮጵያ መሠረት ነው - በለጠ ሞላ (ዶ/ር)
*********************
የአንድ ከተማ ነዋሪዎችን መረጃ በዘመናዊ መንገድ ማደራጀት ሰነድ ከማስቀመጥ ባለፈ የዕለት ተዕለት አገልግሎትን ለማቅለልና ለሀገሪቱ የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ ትልቅ አቅም እንደሚፈጥር የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትሩ በለጠ ሞላ (ዶ/ር) ገለጹ።
ሚኒስትሩ በአዲስ አበባ ከተማ የሲቪል ምዝገባ እና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ ሰነዶችን በዘመናዊና በዲጂታል መንገድ ለማደራጀት እያከናወነ ያለውን ሥራ በአካል ተዘዋውረው ጎብኝተዋል።
በጉብኝታቸውም ወቅት ኢትዮጵያ የጀመረችው የዲጂታላይዜሽን ጉዞ በተግባር መሬት እየረገጠ እንተግባራዊ እየተደረገ መሆኑን ገልጸው፣ በተለይም “ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025” ስትራቴጂ አማካኝነት የተመዘገቡ ስኬቶች ለዚህ ማሳያ ናቸው ብለዋል።
ኤጀንሲ የጀመረው የሰነድ አስተዳደር ሥርዓት ሀገሪቱ ለያዘችው የዲጂታል 2030 ራዕይ መሳካት ትልቅ ስንቅ እንደሚሆንም ገልጸዋል።
ይህም ሥራ በሌሎች የመንግሥት ተቋማት ሊሰፋና ሊቀመር የሚገባ መሆኑን አንስተው፣ ዜጎች ባሉበት ሆነው በቀላሉ መረጃዎችንና አገልግሎቶችን በኦንላይን ማግኘት የሚችሉበትን ሥርዓት ለመዘርጋት ትልቅ ማሳያ መሆኑን አስረድተዋል።
የኤጄንሲው ዋና ዳይሬክተር አቶ ዮሴፍ ንጉሴ በበኩላቸው፣ ተቋሙ በየጊዜው የአገልግሎት አሰጣጡን በማዘመን ላይ እንደሚገኝ ጠቅሰዋል፡፡
በዚህም ከ50 ሚሊዮን በላይ ዲጂታይዝ ከሚደረጉ መረጃዎች ውስጥ በኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ድጋፍ 20 ሚሊዮን የሚሆኑ መረጃዎች ዲጂታይዝ እየተደረጉ መሆኑን አንስተዋል።
በወይንሸት ደጀኔ
#ethiopia #ebc #dijitalethiopia #onlineservice #civilservice
*********************
የአንድ ከተማ ነዋሪዎችን መረጃ በዘመናዊ መንገድ ማደራጀት ሰነድ ከማስቀመጥ ባለፈ የዕለት ተዕለት አገልግሎትን ለማቅለልና ለሀገሪቱ የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ ትልቅ አቅም እንደሚፈጥር የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትሩ በለጠ ሞላ (ዶ/ር) ገለጹ።
ሚኒስትሩ በአዲስ አበባ ከተማ የሲቪል ምዝገባ እና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ ሰነዶችን በዘመናዊና በዲጂታል መንገድ ለማደራጀት እያከናወነ ያለውን ሥራ በአካል ተዘዋውረው ጎብኝተዋል።
በጉብኝታቸውም ወቅት ኢትዮጵያ የጀመረችው የዲጂታላይዜሽን ጉዞ በተግባር መሬት እየረገጠ እንተግባራዊ እየተደረገ መሆኑን ገልጸው፣ በተለይም “ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025” ስትራቴጂ አማካኝነት የተመዘገቡ ስኬቶች ለዚህ ማሳያ ናቸው ብለዋል።
ኤጀንሲ የጀመረው የሰነድ አስተዳደር ሥርዓት ሀገሪቱ ለያዘችው የዲጂታል 2030 ራዕይ መሳካት ትልቅ ስንቅ እንደሚሆንም ገልጸዋል።
ይህም ሥራ በሌሎች የመንግሥት ተቋማት ሊሰፋና ሊቀመር የሚገባ መሆኑን አንስተው፣ ዜጎች ባሉበት ሆነው በቀላሉ መረጃዎችንና አገልግሎቶችን በኦንላይን ማግኘት የሚችሉበትን ሥርዓት ለመዘርጋት ትልቅ ማሳያ መሆኑን አስረድተዋል።
የኤጄንሲው ዋና ዳይሬክተር አቶ ዮሴፍ ንጉሴ በበኩላቸው፣ ተቋሙ በየጊዜው የአገልግሎት አሰጣጡን በማዘመን ላይ እንደሚገኝ ጠቅሰዋል፡፡
በዚህም ከ50 ሚሊዮን በላይ ዲጂታይዝ ከሚደረጉ መረጃዎች ውስጥ በኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ድጋፍ 20 ሚሊዮን የሚሆኑ መረጃዎች ዲጂታይዝ እየተደረጉ መሆኑን አንስተዋል።
በወይንሸት ደጀኔ
#ethiopia #ebc #dijitalethiopia #onlineservice #civilservice
3 days ago
በ2019 ዓ.ም የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ የ10.1 በመቶ ዕድገት ያስመዘግባል - አቶ አሕመድ ሺዴ
ኢትዮጵያ ከይፋዊ አበዳሪዎች ጋር የተጀመረው የውጭ ዕዳ ሽግሽግ ስምምነት ወደ ማጠናቀቂያው ምዕራፍ ላይ መድረሱን የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አሕመድ ሺዴ ገልጸዋል።
ሚኒስትሩ ይህንን የገለጹት በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 25ኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ የ2019 በጀት ዓመት መነሻ ዕቅድን ለውይይት ባቀረቡበት ወቅት ነው።
የመንግሥትን የውጭ ብድር ጤናማ ለማድረግ በቡድን 20 የጋራ ማዕቀፍ ስር የተጀመረው የዕዳ ሽግሽግ ሂደት በርካታ ስኬቶች የተመዘገቡበት መሆኑን ጠቅሰዋል።
እንደ ሚኒስትሩ ገለጻ በዋና ዋና የፋይናንስ መለኪያዎች ላይ የተደረሰውን ስምምነት መሠረት በማድረግ የመግባቢያ ሰነድ የተፈረመ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት ከአብዛኞቹ አበዳሪዎች ጋር የሁለትዮሽ የዕዳ ሽግሽግ ስምምነቶች ተፈርሟል።
ከዩሮቦንድ እና ከሌሎች አበዳሪዎች ጋር የሚደረገው ድርድርም ስምምነት ላይ ለመድረስ መቃረቡን ሚኒስትሩ ገልጸዋል፡፡
ይህም በየዓመቱ ለዕዳ ክፍያ የሚውለውን የውጭ ምንዛሬ ጫና በመቀነሱ ለኢትዮጵያ የልማት ፋይናንስ ተጨማሪ ሀብት ለማዋል ማገዙን እና የሀገራችን የዕዳ ጫና ስጋት ወደ መካከለኛ ደረጃ ዝቅ እንደሚያደርገው አስረድተዋል።
በመጠናቀቅ ላይ ባለዉ 2018 በጀት ዓመት የመንግሥት የልማት ድርጅቶችን ምርታማነት እና ተወዳዳሪነት ለማሳደግ የሚከናወኑ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን አቶ አሕመድ ጠቅሰዋል፡፡
በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ አማካኝነት ከግሉ ዘርፍ ጋር በመቀናጀት በታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ የማዳበሪያ ፋብሪካ ግንባታ ፕሮጀክት መጀመሩን እና በኢትዮጵያ አየር መንገድ የሚከናወነውን የቢሾፍቱ ኢንተርናሽናል አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታ ፕሮጀክትን በዋነኛነት ጠቅሰዋል።
በኢትዮጵያ እየታየ ያለው አጠቃላይ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ ካለፉት ዓመታት እጅግ የተሻለ መሆኑን የጠቀሱት ሚኒስትሩ፣ በዚህም መሰረት በ2019 በጀት ዓመትም የ10.1 በመቶ የኢኮኖሚ ዕድገት እንደሚመዘገብ ግምት መወሰዱን ተናግረዋል፡፡
#ebc
ኢትዮጵያ ከይፋዊ አበዳሪዎች ጋር የተጀመረው የውጭ ዕዳ ሽግሽግ ስምምነት ወደ ማጠናቀቂያው ምዕራፍ ላይ መድረሱን የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አሕመድ ሺዴ ገልጸዋል።
ሚኒስትሩ ይህንን የገለጹት በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 25ኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ የ2019 በጀት ዓመት መነሻ ዕቅድን ለውይይት ባቀረቡበት ወቅት ነው።
የመንግሥትን የውጭ ብድር ጤናማ ለማድረግ በቡድን 20 የጋራ ማዕቀፍ ስር የተጀመረው የዕዳ ሽግሽግ ሂደት በርካታ ስኬቶች የተመዘገቡበት መሆኑን ጠቅሰዋል።
እንደ ሚኒስትሩ ገለጻ በዋና ዋና የፋይናንስ መለኪያዎች ላይ የተደረሰውን ስምምነት መሠረት በማድረግ የመግባቢያ ሰነድ የተፈረመ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት ከአብዛኞቹ አበዳሪዎች ጋር የሁለትዮሽ የዕዳ ሽግሽግ ስምምነቶች ተፈርሟል።
ከዩሮቦንድ እና ከሌሎች አበዳሪዎች ጋር የሚደረገው ድርድርም ስምምነት ላይ ለመድረስ መቃረቡን ሚኒስትሩ ገልጸዋል፡፡
ይህም በየዓመቱ ለዕዳ ክፍያ የሚውለውን የውጭ ምንዛሬ ጫና በመቀነሱ ለኢትዮጵያ የልማት ፋይናንስ ተጨማሪ ሀብት ለማዋል ማገዙን እና የሀገራችን የዕዳ ጫና ስጋት ወደ መካከለኛ ደረጃ ዝቅ እንደሚያደርገው አስረድተዋል።
በመጠናቀቅ ላይ ባለዉ 2018 በጀት ዓመት የመንግሥት የልማት ድርጅቶችን ምርታማነት እና ተወዳዳሪነት ለማሳደግ የሚከናወኑ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን አቶ አሕመድ ጠቅሰዋል፡፡
በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ አማካኝነት ከግሉ ዘርፍ ጋር በመቀናጀት በታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ የማዳበሪያ ፋብሪካ ግንባታ ፕሮጀክት መጀመሩን እና በኢትዮጵያ አየር መንገድ የሚከናወነውን የቢሾፍቱ ኢንተርናሽናል አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታ ፕሮጀክትን በዋነኛነት ጠቅሰዋል።
በኢትዮጵያ እየታየ ያለው አጠቃላይ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ ካለፉት ዓመታት እጅግ የተሻለ መሆኑን የጠቀሱት ሚኒስትሩ፣ በዚህም መሰረት በ2019 በጀት ዓመትም የ10.1 በመቶ የኢኮኖሚ ዕድገት እንደሚመዘገብ ግምት መወሰዱን ተናግረዋል፡፡
#ebc
4 days ago
አዲሱ የተሽከርካሪ ሰሌዳ በአዲስ አበባ ተመዝግበው ሰሌዳ እየተጠባበቁ ባሉ አዳዲስ ተሽከርካሪዎች ላይ ከዛሬ ጀምሮ ተግባራዊ መደረግ ጀምሯል
ይህ የአዲሱ ተሽከርካሪ ሰሌዳ ETH የሚል አለምአቀፋዊ ኮድ የያዘ መሆኑ የተገለፀ ሲሆን የአተገባበር ሂደቱ በአዲስ አበባ መጀመሩ ተገልፆል።
የታርጋ ዋጋዉን በተመለከተ የወጣ ስትራቴጂ ያለ መሆኑን እና ህዝብ በብዛት የሚጠቀማቸው የብዙሃን ትራንስፓርት እና የግል ተሽከርካሪዎች የሰሌዳ ዋጋዉ ላይ ልዩነት እንደሚኖር ሰምተናል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የአሽከርካሪ እና ተሽከርካሪ ቁጥጥር ባለስልጣን የአዲሱ የተሽከርካሪ ሰሌዳ ይዘት÷ አተገባበር እና አስፈላጊነት ዙሪያ ለመገናኛ ብዙሃን ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቷል።
ባለስልጣኑ በመግለጫዉ በመዲናይቱ አሁን ላይ ተመዝግበው ሰሌዳ በመጠባበቅ ላይ የሚገኙ ተሽከርካሪ ላይ ተግባራዊ እንዲሆን መወሰኑ ተገልፆል።
የመጀመሪያዉ ሰሌዳ ባለስልጣኑ ካሉት 11 ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤቶች አንዱ በሆነዉ የየካ ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት መሰጠቱ ተነግሯል።
መግለጫዉን የሰጡት የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር አቶ ዘገየ በላይነህ እንደገለፁት አዲሱ የሰሌዳ ሀገራዊ ይዘት ያለዉ እንዲሁም ሰሌዳዉ ፎርጂድ አይሰራም ብለን እናምናለን ሲሉ ገልፀዋል።
አዲሱ የተሽከርካሪ ሰሌዳ ለህግ ማስከበር የሚመች እና ምን አይነት ተሽከርካሪ እና የተሽከርካሪ ባለቤት ማነዉ የሚል ማሳያዎችን ይዟል ተብሏል።
የረዥም ጊዜ የሚያገለግል እና የሀብት ብክነት የሚቀንስ መሆኑ አንድ ተሽከርካሪ አንድ ሰሌዳ ብቻ የሚጠቀም የሚያደርግ ነዉ ሲል ባለስልጣኑ በመግለጫው ተነግሯል።
አዲሱ ሰሌዳ ተሽከርካሪዉ እስኪወገድ ድረስ የሚያገለግል ይሆናል ያለዉ ባለስልጣኑ ከ800 ሺህ በላይ ተሽከርካሪዎች አሉ ሰሌዳዉ ተወስዶ መች ይጠናቀቃል በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የሚወሰን ይሆናል ተብሏል።
በሁሉም ተሽከርካሪዎች አዲሱን ሰሌዳ ተግባራዊ ለማድረግ በትራንስፖርት እና ሎጀስቲክ ሚኒስቴር በሚያስቀምጣቸው የጊዜ እቅድ ሰሌዳዉን የመቀየር ሂደቱ እንደሚተገበር ነዉ የተገለፀው።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የአሽከርካሪ እና ተሽከርካሪ ቁጥጥር ባለስልጣን 1050/2017 መመሪያን በዛሬዉ እለት መተግበር መጀመሩን አሳዉቋል።
ቁምነገር አየለ
ይህ የአዲሱ ተሽከርካሪ ሰሌዳ ETH የሚል አለምአቀፋዊ ኮድ የያዘ መሆኑ የተገለፀ ሲሆን የአተገባበር ሂደቱ በአዲስ አበባ መጀመሩ ተገልፆል።
የታርጋ ዋጋዉን በተመለከተ የወጣ ስትራቴጂ ያለ መሆኑን እና ህዝብ በብዛት የሚጠቀማቸው የብዙሃን ትራንስፓርት እና የግል ተሽከርካሪዎች የሰሌዳ ዋጋዉ ላይ ልዩነት እንደሚኖር ሰምተናል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የአሽከርካሪ እና ተሽከርካሪ ቁጥጥር ባለስልጣን የአዲሱ የተሽከርካሪ ሰሌዳ ይዘት÷ አተገባበር እና አስፈላጊነት ዙሪያ ለመገናኛ ብዙሃን ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቷል።
ባለስልጣኑ በመግለጫዉ በመዲናይቱ አሁን ላይ ተመዝግበው ሰሌዳ በመጠባበቅ ላይ የሚገኙ ተሽከርካሪ ላይ ተግባራዊ እንዲሆን መወሰኑ ተገልፆል።
የመጀመሪያዉ ሰሌዳ ባለስልጣኑ ካሉት 11 ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤቶች አንዱ በሆነዉ የየካ ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት መሰጠቱ ተነግሯል።
መግለጫዉን የሰጡት የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር አቶ ዘገየ በላይነህ እንደገለፁት አዲሱ የሰሌዳ ሀገራዊ ይዘት ያለዉ እንዲሁም ሰሌዳዉ ፎርጂድ አይሰራም ብለን እናምናለን ሲሉ ገልፀዋል።
አዲሱ የተሽከርካሪ ሰሌዳ ለህግ ማስከበር የሚመች እና ምን አይነት ተሽከርካሪ እና የተሽከርካሪ ባለቤት ማነዉ የሚል ማሳያዎችን ይዟል ተብሏል።
የረዥም ጊዜ የሚያገለግል እና የሀብት ብክነት የሚቀንስ መሆኑ አንድ ተሽከርካሪ አንድ ሰሌዳ ብቻ የሚጠቀም የሚያደርግ ነዉ ሲል ባለስልጣኑ በመግለጫው ተነግሯል።
አዲሱ ሰሌዳ ተሽከርካሪዉ እስኪወገድ ድረስ የሚያገለግል ይሆናል ያለዉ ባለስልጣኑ ከ800 ሺህ በላይ ተሽከርካሪዎች አሉ ሰሌዳዉ ተወስዶ መች ይጠናቀቃል በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የሚወሰን ይሆናል ተብሏል።
በሁሉም ተሽከርካሪዎች አዲሱን ሰሌዳ ተግባራዊ ለማድረግ በትራንስፖርት እና ሎጀስቲክ ሚኒስቴር በሚያስቀምጣቸው የጊዜ እቅድ ሰሌዳዉን የመቀየር ሂደቱ እንደሚተገበር ነዉ የተገለፀው።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የአሽከርካሪ እና ተሽከርካሪ ቁጥጥር ባለስልጣን 1050/2017 መመሪያን በዛሬዉ እለት መተግበር መጀመሩን አሳዉቋል።
ቁምነገር አየለ
Sponsored by
Surafel
4 days ago
የበጀት ጉድለቱ በ7 ዓመታት ውስጥ ዝቅተኛው ደረጃ ላይ ደርሷል - የገንዘብ ሚኒስቴር
******************
በኢትዮጵያ ተግባራዊ የተደረገውን የተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ተከትሎ የኢትዮጵያ የታክስ ገቢ ከጠቅላላ የሀገር ውስጥ ምርት (GDP) ያለው ድርሻ በ2018 በጀት ዓመት ወደ 9.5 በመቶ ከፍ ይላል ተብሎ እንደሚጠበቅ የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አሕመድ ሺዴ አስታወቁ።
ሚኒስትሩ ይህንን የገለጹት ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 25ኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ የ2019 በጀት ዓመት መነሻ ዕቅድን ለውይይት ባቀረቡበት ወቅት ነው።
አቶ አሕመድ ሽዴ ለምክር ቤቱ እንደገለጹት፣ የግብር አሰባሰብን ለማሳለጥ እና የታክስ ፍትሐዊነትን ለማረጋገጥ የወጣው ብሔራዊ የመካከለኛ ዘመን ስትራቴጂ ውጤት እያስገኘ ነው።
በዚህም መሠረት ከበርካታ ዓመታት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ በ2017 በጀት ዓመት ሀገራዊ የታክስ ገቢ ከጠቅላላ የሀገር ውስጥ ምርት ጋር ያለው ጥምርታ በ1.6 በመቶ በመጨመር፣ በ2016 ከነበረበት 6.2 በመቶ ወደ 7.7 በመቶ ከፍ ማለቱን አብራርተዋል።
ይህ አፈጻጸም በ2018 በጀት ዓመትም ተጠናክሮ በመቀጠሉ ድርሻው ወደ 9.5 በመቶ ያድጋል ተብሎ እንደሚገመት አመልክተዋል።
ለዚህ ስኬት የተጨማሪ እሴት ታክስ፣ የኤክሳይዝ ታክስ እና የገቢ ግብር አዋጅ ማሻሻያዎች እንዲሁም የኢንቨስትመንት ማበረታቻ ሥርዓት ማሻሻያ መደረጉ በዋናነት ይጠቀሳሉ።
ሚኒስትሩ አክለውም ከዚህ ቀደም በጥቅሉ ሲሰጡ የነበሩ እና ተገቢውን ውጤት የማያመጡ የኢንቨስትመንት ማበረታቻዎችን በመቀነስ፣ ማበረታቻው ኢንቨስተሮች በሀገር ውስጥ ከሚያስመዘግቡት የሥራ ዕድል፣ የቴክኖሎጂ ሽግግር እና የካፒታል ፈጠራ ጋር በቀጥታ እንዲገናኝ መደረጉ ሀገራችን ታጣው የነበረውን ከፍተኛ ገቢ ለማስቀረት ማስቻሉን ገልጸዋል።
በሌላ በኩል የመንግሥት የፊስካል ጉድለት መጠን ከፍተኛ መሻሻል ማሳየቱን የጠቀሱት አቶ አሕመድ በ2017 በጀት ዓመት በ7 ዓመታት ውስጥ ዝቅተኛው የበጀት ጉድለት መመዝገቡን ይፋ አድርገዋል።
ይህም ከአጠቃላይ ሀገራዊ ምርት (GDP) አኳያ አንድ በመቶ ብቻ መሆኑን እና በ2014 ዓ.ም ከነበረበት 4.1 በመቶ አንጻር ሲታይ እጅግ ከፍተኛ መሻሻል መሆኑን አስረድተዋል።
በበረከት ሽመልስ
#ethiopia #ebc #economy #budget
******************
በኢትዮጵያ ተግባራዊ የተደረገውን የተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ተከትሎ የኢትዮጵያ የታክስ ገቢ ከጠቅላላ የሀገር ውስጥ ምርት (GDP) ያለው ድርሻ በ2018 በጀት ዓመት ወደ 9.5 በመቶ ከፍ ይላል ተብሎ እንደሚጠበቅ የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አሕመድ ሺዴ አስታወቁ።
ሚኒስትሩ ይህንን የገለጹት ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 25ኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ የ2019 በጀት ዓመት መነሻ ዕቅድን ለውይይት ባቀረቡበት ወቅት ነው።
አቶ አሕመድ ሽዴ ለምክር ቤቱ እንደገለጹት፣ የግብር አሰባሰብን ለማሳለጥ እና የታክስ ፍትሐዊነትን ለማረጋገጥ የወጣው ብሔራዊ የመካከለኛ ዘመን ስትራቴጂ ውጤት እያስገኘ ነው።
በዚህም መሠረት ከበርካታ ዓመታት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ በ2017 በጀት ዓመት ሀገራዊ የታክስ ገቢ ከጠቅላላ የሀገር ውስጥ ምርት ጋር ያለው ጥምርታ በ1.6 በመቶ በመጨመር፣ በ2016 ከነበረበት 6.2 በመቶ ወደ 7.7 በመቶ ከፍ ማለቱን አብራርተዋል።
ይህ አፈጻጸም በ2018 በጀት ዓመትም ተጠናክሮ በመቀጠሉ ድርሻው ወደ 9.5 በመቶ ያድጋል ተብሎ እንደሚገመት አመልክተዋል።
ለዚህ ስኬት የተጨማሪ እሴት ታክስ፣ የኤክሳይዝ ታክስ እና የገቢ ግብር አዋጅ ማሻሻያዎች እንዲሁም የኢንቨስትመንት ማበረታቻ ሥርዓት ማሻሻያ መደረጉ በዋናነት ይጠቀሳሉ።
ሚኒስትሩ አክለውም ከዚህ ቀደም በጥቅሉ ሲሰጡ የነበሩ እና ተገቢውን ውጤት የማያመጡ የኢንቨስትመንት ማበረታቻዎችን በመቀነስ፣ ማበረታቻው ኢንቨስተሮች በሀገር ውስጥ ከሚያስመዘግቡት የሥራ ዕድል፣ የቴክኖሎጂ ሽግግር እና የካፒታል ፈጠራ ጋር በቀጥታ እንዲገናኝ መደረጉ ሀገራችን ታጣው የነበረውን ከፍተኛ ገቢ ለማስቀረት ማስቻሉን ገልጸዋል።
በሌላ በኩል የመንግሥት የፊስካል ጉድለት መጠን ከፍተኛ መሻሻል ማሳየቱን የጠቀሱት አቶ አሕመድ በ2017 በጀት ዓመት በ7 ዓመታት ውስጥ ዝቅተኛው የበጀት ጉድለት መመዝገቡን ይፋ አድርገዋል።
ይህም ከአጠቃላይ ሀገራዊ ምርት (GDP) አኳያ አንድ በመቶ ብቻ መሆኑን እና በ2014 ዓ.ም ከነበረበት 4.1 በመቶ አንጻር ሲታይ እጅግ ከፍተኛ መሻሻል መሆኑን አስረድተዋል።
በበረከት ሽመልስ
#ethiopia #ebc #economy #budget
4 days ago
ትራምፕ ለኢራን የመጨረሻ ማስጠንቀቂያ ሰጡ‼️
👉ሆርሙዝ ሙሉ ለሙሉ ተዘግቷል-ኢራን‼️
#አሜሪካ በኢራን ላይ አዳሯን ከባድ ጥቃት አደረሠች።
# ዋሽንግተን በቶማሃውክ ሚሳኤል ጭምር እስከ #ቴህራን አቅራቢያ ጥቃት ማድረሷን በፕሬዚዳንቷ በኩል ገልፃለች።
#ኢራንም በምላሹ በጆርዳን እና ኩዬት በሚገኙ የአሜሪካ የጦር ቤዞች ላይ ከ12 በላይ ሚሳይል እና ድሮን በመጠቀም ጥቃት ሰንዝራለች።
በሆርሙዝ ሰርጥም ሁለት መርከቦችን መትቻለሁ” ብላለች።
የአሜሪካን ጥቃት ተከትሎ ኢራን #በሆርሙዝ ሰርጥ የሚያልፍ የትኛውም ዓይነት መርከብ አይኖርም ያለችው ሰርጡ ሙሉ በሙሉ ተዘግቷል ስትል በጦር ቃል አቀባያዋ በኩል ይፋ አድርጋለች።
ኢራን ሆርሙዝ ሙሉ ለሙሉ ተዘግቧል ካለች በኋላ አለምአቀፍ የድፍድፍ ነዳጅ ዋጋ የ 2 ዶላር ጭማሪ አሳይቷል።
የአሜሪካ የቀጠናው ዕዝ ግን የንግድ መርከቦች አሁንም በሆርሙዝ እያለፉ ነው ሲል መግለጫ ሰጥቷል።
አሜሪካ በምሽቱ ጥቃት 49 አቶማሃውክ ሚሳዔሎችን በመጠቀም 18 ኢላማዎችን መምታታቸውን ትራምፕ አሳውቀዋል።
ዛሬ ሰኔ 4/2018 ዓ.ም ኢራን ወደ ስምምነት ካልመጣች ከምድረ ገፅ ይጠፋሉ ሲሉ ትራምፕ ማስጠንቀቂያ ልከዋል።
Seledadotio
Seledadotio
👉ሆርሙዝ ሙሉ ለሙሉ ተዘግቷል-ኢራን‼️
#አሜሪካ በኢራን ላይ አዳሯን ከባድ ጥቃት አደረሠች።
# ዋሽንግተን በቶማሃውክ ሚሳኤል ጭምር እስከ #ቴህራን አቅራቢያ ጥቃት ማድረሷን በፕሬዚዳንቷ በኩል ገልፃለች።
#ኢራንም በምላሹ በጆርዳን እና ኩዬት በሚገኙ የአሜሪካ የጦር ቤዞች ላይ ከ12 በላይ ሚሳይል እና ድሮን በመጠቀም ጥቃት ሰንዝራለች።
በሆርሙዝ ሰርጥም ሁለት መርከቦችን መትቻለሁ” ብላለች።
የአሜሪካን ጥቃት ተከትሎ ኢራን #በሆርሙዝ ሰርጥ የሚያልፍ የትኛውም ዓይነት መርከብ አይኖርም ያለችው ሰርጡ ሙሉ በሙሉ ተዘግቷል ስትል በጦር ቃል አቀባያዋ በኩል ይፋ አድርጋለች።
ኢራን ሆርሙዝ ሙሉ ለሙሉ ተዘግቧል ካለች በኋላ አለምአቀፍ የድፍድፍ ነዳጅ ዋጋ የ 2 ዶላር ጭማሪ አሳይቷል።
የአሜሪካ የቀጠናው ዕዝ ግን የንግድ መርከቦች አሁንም በሆርሙዝ እያለፉ ነው ሲል መግለጫ ሰጥቷል።
አሜሪካ በምሽቱ ጥቃት 49 አቶማሃውክ ሚሳዔሎችን በመጠቀም 18 ኢላማዎችን መምታታቸውን ትራምፕ አሳውቀዋል።
ዛሬ ሰኔ 4/2018 ዓ.ም ኢራን ወደ ስምምነት ካልመጣች ከምድረ ገፅ ይጠፋሉ ሲሉ ትራምፕ ማስጠንቀቂያ ልከዋል።
Seledadotio
Seledadotio
Comments