9 hours ago
አልማ ለ2019 በጀት ዓመት ከ4.3 ቢሊዮን ብር በላይ የልማት ሀብት ለማሰባሰብ አቀደ
#ethiopia | የአማራ ልማት ማህበር (አልማ) የ2018 በጀት ዓመት አፈጻጸምን በመገምገም የ2019 በጀት ዓመት ዕቅዱን ያስተዋወቀ ሲሆን፣ የዕቅዱን ስኬት ለማረጋገጥ የቅድመ ዝግጅት ምዕራፍን በሙሉ ማጠናቀቅ እንደሚገባ ዋና ሥራ አስፈጻሚው አቶ መላኩ ፈንታ አሳስበዋል።
በዋና መሥሪያ ቤቱ ለሁለት ቀናት በተካሄደው የምክክር መድረክ፣ ከ11 ዞኖች የተውጣጡ የማኔጅመንት አባላትና የወረዳ ጽሕፈት ቤት ኃላፊዎች ተሳትፈው በቀጣዩ ዓመት የሚተገበሩ ዋና ዋና የልማት ፕሮጀክቶች ላይ ተወያይተዋል።
ስትራቴጂክና ኢኖቬሽን ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ አበረ መኩሪያ እንደገለጹት፣ በ2019 በጀት ዓመት ከአባላት 4.3 ቢሊዮን ብር፣ ከዳያስፖራ ከ34 ሚሊዮን ዶላር በላይ እና ከአጋር ተቋማት 55 ሚሊዮን ዶላር የልማት ሀብት ለማሰባሰብ ታቅዷል።
በተያዘው ዕቅድ 2,051 የመማሪያ ክፍሎች፣ 38 የጤና ተቋማት፣ 8 የቴክኒክ ኮሌጅ ወርክሾፖች እና 2 ሸዶች እንዲገነቡ ታቅዷል። ይህን ግዙፍ ዕቅድ ለማሳካት የህዝብ ተሳትፎን ማሳደግ፣ ከአጋር አካላትና ከዳያስፖራው ጋር የተጠናከረ ትብብር መፍጠር ወሳኝ መሆኑ ተገልጿል።
አቶ መላኩ ፈንታ በማጠቃለያ ንግግራቸው፣ በ2019 በጀት ዓመት የዲጂታል ሽግግርን ማፋጠን፣ የአፈጻጸም ጥራትን ማሻሻል፣ የተቋሙን ብራንድ ማጠናከርና ዘላቂ የፋይናንስ አቅም መፍጠር ዋና ትኩረቶች እንደሚሆኑ ገልጸዋል።
በመድረኩ መጨረሻ በ2018 በጀት ዓመት የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ የዞንና የወረዳ አልማ ጽሕፈት ቤቶች፣ እንዲሁም ለተመራጭ ሠራተኞች የማበረታቻ ሽልማትና የምስክር ወረቀት ተሰጥቷል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#ethiopia | የአማራ ልማት ማህበር (አልማ) የ2018 በጀት ዓመት አፈጻጸምን በመገምገም የ2019 በጀት ዓመት ዕቅዱን ያስተዋወቀ ሲሆን፣ የዕቅዱን ስኬት ለማረጋገጥ የቅድመ ዝግጅት ምዕራፍን በሙሉ ማጠናቀቅ እንደሚገባ ዋና ሥራ አስፈጻሚው አቶ መላኩ ፈንታ አሳስበዋል።
በዋና መሥሪያ ቤቱ ለሁለት ቀናት በተካሄደው የምክክር መድረክ፣ ከ11 ዞኖች የተውጣጡ የማኔጅመንት አባላትና የወረዳ ጽሕፈት ቤት ኃላፊዎች ተሳትፈው በቀጣዩ ዓመት የሚተገበሩ ዋና ዋና የልማት ፕሮጀክቶች ላይ ተወያይተዋል።
ስትራቴጂክና ኢኖቬሽን ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ አበረ መኩሪያ እንደገለጹት፣ በ2019 በጀት ዓመት ከአባላት 4.3 ቢሊዮን ብር፣ ከዳያስፖራ ከ34 ሚሊዮን ዶላር በላይ እና ከአጋር ተቋማት 55 ሚሊዮን ዶላር የልማት ሀብት ለማሰባሰብ ታቅዷል።
በተያዘው ዕቅድ 2,051 የመማሪያ ክፍሎች፣ 38 የጤና ተቋማት፣ 8 የቴክኒክ ኮሌጅ ወርክሾፖች እና 2 ሸዶች እንዲገነቡ ታቅዷል። ይህን ግዙፍ ዕቅድ ለማሳካት የህዝብ ተሳትፎን ማሳደግ፣ ከአጋር አካላትና ከዳያስፖራው ጋር የተጠናከረ ትብብር መፍጠር ወሳኝ መሆኑ ተገልጿል።
አቶ መላኩ ፈንታ በማጠቃለያ ንግግራቸው፣ በ2019 በጀት ዓመት የዲጂታል ሽግግርን ማፋጠን፣ የአፈጻጸም ጥራትን ማሻሻል፣ የተቋሙን ብራንድ ማጠናከርና ዘላቂ የፋይናንስ አቅም መፍጠር ዋና ትኩረቶች እንደሚሆኑ ገልጸዋል።
በመድረኩ መጨረሻ በ2018 በጀት ዓመት የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ የዞንና የወረዳ አልማ ጽሕፈት ቤቶች፣ እንዲሁም ለተመራጭ ሠራተኞች የማበረታቻ ሽልማትና የምስክር ወረቀት ተሰጥቷል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
9 hours ago
አዲሱ ተርሚናል የአማራ ክልልን ቱሪዝምና ኢንቨስትመንት በማበልፀግ ቁልፍ ሚና ይጫወታል፦ አቶ መስፍን ጣሰው
*******************
የኢትዮጵያ አየር መንገድ በባህር ዳር ደጃዝማች በላይ ዘለቀ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በ4.1 ቢሊዮን ብር ወጪ ያስገነባው ዘመናዊ የመንገደኞች ማስተናገጃ ተርሚናል ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል።
ዋና ሥራ አስፈጻሚ መስፍን ጣሰው በዚሁ ወቅት እንዳሉት፣ ባህር ዳር ከቀድሞው የጎጃም ክፍለ ሀገር እስከ አሁኑ የአማራ ክልል ዋና ከተማነቷ ላሳየችው ዕድገት ከ60 ዓመታት በፊት ወደ ከተማዋ በረራ የጀመረው የኢትዮጵያ አየር መንገድ የላቀ ሚና ተጫውቷል።
ይህ በ8 ሺህ 300 ካሬ ሜትር ቦታ ላይ ያረፈው እና ጠቅላላ የወለል ስፋቱ 11 ሺህ 170 ካሬ ሜትር የሆነው አዲሱ ተርሚናል፣ ከቦሌ አውሮፕላን ማረፊያ ቀጥሎ ትልቁ የሀገር ውስጥ ተርሚናል መሆኑን አቶ መስፍን ጠቅሰዋል።
ተርሚናሉ በአንድ ጊዜ እስከ 700 መንገደኞችን የማስተናገድ አቅም ያለው ሲሆን፣ ሰፊ የቪአይፒ ሳሎኖችን፣ የክቡር መንገደኞች ላውንጆችን እና ምግብ ቤቶችን ጭምር ያካተተ መሆኑንም አክለዋል።
በተደረገለት የኤፕሮን ማስፋፊያ አሁን ላይ በአንድ ጊዜ እንደ ቦይንግ 777 ያሉ 4 ትላልቅ እና እንደ ቦይንግ 737 ያሉ 6 መለስተኛ አውሮፕላኖችን ማቆም የሚያስችል አቅም ያለው ተርሚናሉ፣ ወደፊት በትንሽ ማስተካከያ ዓለም አቀፍ እና የሀገር ውስጥ መንገደኞችን በተጓዳኝ ማስተናገድ ይችላል ብለዋል።
አየር መንገዱ ወደ ባህር ዳር በቀን እስከ 14 የበረራ ምልልሶችን እንደሚያደርግ ጠቅሰው፤ የተርሚናሉ መገንባት በክልሉ ቱሪዝም፣ ንግድና ኢንቨስትመንት እንዲስፋፋ ከማድረግ ባሻገር ከተማዋ የኮንፈረንስች ማዕከል እንድትሆን ያግዛል ብለዋል።
አየር መንገዱ ባለፈው አንድ ዓመት ውስጥ አራት አዳዲስ አውሮፕላን ማረፊያዎችን ገንብቶ አገልግሎት ላይ ማዋሉን እና አምስተኛው በመቱ በሚመጡት ሁለት ወራት ውስጥ እንደሚጠናቀቅ ገልጸው፤ የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታም በታቀደለት የጊዜ ሰሌዳ እየተፋጠነ መሆኑን አረጋግጠዋል።
ዋና ሥራ አስፈጻሚው ለፕሮጀክቱ ስኬት የላቀ አስተዋጽኦ ላደረጉት ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶር) እና ለኢፌዴሪ መንግሥት እንዲሁም ለቻይናው ሳኢኖ ሃይድሮ፣ ለአማካሪው ዳር አልሀንዳሳ፣ ለአየር መንገዱ መሀንዲሶች፣ ለአማራ ክልል እና ለባህር ዳር ከተማ አስተዳደር ልባዊ ምስጋና አቅርበዋል።
በሔዋን ጌታቸው
#ethiopia #aviation #ethiopianairlines #bahirdar #airport #ebc
*******************
የኢትዮጵያ አየር መንገድ በባህር ዳር ደጃዝማች በላይ ዘለቀ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በ4.1 ቢሊዮን ብር ወጪ ያስገነባው ዘመናዊ የመንገደኞች ማስተናገጃ ተርሚናል ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል።
ዋና ሥራ አስፈጻሚ መስፍን ጣሰው በዚሁ ወቅት እንዳሉት፣ ባህር ዳር ከቀድሞው የጎጃም ክፍለ ሀገር እስከ አሁኑ የአማራ ክልል ዋና ከተማነቷ ላሳየችው ዕድገት ከ60 ዓመታት በፊት ወደ ከተማዋ በረራ የጀመረው የኢትዮጵያ አየር መንገድ የላቀ ሚና ተጫውቷል።
ይህ በ8 ሺህ 300 ካሬ ሜትር ቦታ ላይ ያረፈው እና ጠቅላላ የወለል ስፋቱ 11 ሺህ 170 ካሬ ሜትር የሆነው አዲሱ ተርሚናል፣ ከቦሌ አውሮፕላን ማረፊያ ቀጥሎ ትልቁ የሀገር ውስጥ ተርሚናል መሆኑን አቶ መስፍን ጠቅሰዋል።
ተርሚናሉ በአንድ ጊዜ እስከ 700 መንገደኞችን የማስተናገድ አቅም ያለው ሲሆን፣ ሰፊ የቪአይፒ ሳሎኖችን፣ የክቡር መንገደኞች ላውንጆችን እና ምግብ ቤቶችን ጭምር ያካተተ መሆኑንም አክለዋል።
በተደረገለት የኤፕሮን ማስፋፊያ አሁን ላይ በአንድ ጊዜ እንደ ቦይንግ 777 ያሉ 4 ትላልቅ እና እንደ ቦይንግ 737 ያሉ 6 መለስተኛ አውሮፕላኖችን ማቆም የሚያስችል አቅም ያለው ተርሚናሉ፣ ወደፊት በትንሽ ማስተካከያ ዓለም አቀፍ እና የሀገር ውስጥ መንገደኞችን በተጓዳኝ ማስተናገድ ይችላል ብለዋል።
አየር መንገዱ ወደ ባህር ዳር በቀን እስከ 14 የበረራ ምልልሶችን እንደሚያደርግ ጠቅሰው፤ የተርሚናሉ መገንባት በክልሉ ቱሪዝም፣ ንግድና ኢንቨስትመንት እንዲስፋፋ ከማድረግ ባሻገር ከተማዋ የኮንፈረንስች ማዕከል እንድትሆን ያግዛል ብለዋል።
አየር መንገዱ ባለፈው አንድ ዓመት ውስጥ አራት አዳዲስ አውሮፕላን ማረፊያዎችን ገንብቶ አገልግሎት ላይ ማዋሉን እና አምስተኛው በመቱ በሚመጡት ሁለት ወራት ውስጥ እንደሚጠናቀቅ ገልጸው፤ የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታም በታቀደለት የጊዜ ሰሌዳ እየተፋጠነ መሆኑን አረጋግጠዋል።
ዋና ሥራ አስፈጻሚው ለፕሮጀክቱ ስኬት የላቀ አስተዋጽኦ ላደረጉት ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶር) እና ለኢፌዴሪ መንግሥት እንዲሁም ለቻይናው ሳኢኖ ሃይድሮ፣ ለአማካሪው ዳር አልሀንዳሳ፣ ለአየር መንገዱ መሀንዲሶች፣ ለአማራ ክልል እና ለባህር ዳር ከተማ አስተዳደር ልባዊ ምስጋና አቅርበዋል።
በሔዋን ጌታቸው
#ethiopia #aviation #ethiopianairlines #bahirdar #airport #ebc
10 hours ago
ሃምሣ ዓመታትን የዘለቀ የተቃርኖ እና የደባ ጉዞ
*********************
የከሰረው የህወሓት ቡድን ከተፈጠረበት ዘመን አንሥቶ እስካሁን ድረስ የሚናገረው ሌላ፣ የሚያደርገው ሌላ የሆነ የተቃርኖ ፖለቲካ ቁንጮ ነው።
ብዙ ጊዜ በጽሑፍ ማንነቱን ሲገልጽ የነበረ ቢሆንም፣ ይህ ስብስብ በእውነተኛ ትርጉሙ የፖለቲካ ፓርቲ ወይም የሀገር መሪ ሆኖ አያውቅም። ይልቁንም ላለፉት አምስት ዐሥርት ዓመታት፣ ክልልንም ሆነ ሀገርን ጨምድዶ በመያዝ እንደ አንድ የሽፍታ ቡድን የሚያስብ፣ በጥቂት ቤተሰቦች የጥቅም ትሥሥር የሚዘወር ማፍያዊ ስብስብ ነው።
ድሮም ሆነ አሁን ለፍላጎቱ ያልተገዙትን የሚጨቁን፣ ትብብርን የሚጠላ፣ የሚያጠፋ፣ የሚበትን እና የሚገድል፤ የጥላቻ ቁንጮ የሆነ፣ ፀረ አንድነት እና ፀረ ኅብረ ብሔራዊነት የተጠናወተው ቡድን ነው። ይህ ቡድን በ1968 ዓ.ም ባወጣው ማኒፌስቶው እውነተኛ ፀረ ሕዝብ ማንነቱን አሳይቷል።
የኢትዮጵያ ታሪክ ዋልታ የሆነውን፣ የጠንካራ ኢትዮጵያዊነት መሠረት የሆነውን የትግራይን ሕዝብ ከኢትዮጵያ ነጥሎ ለማኖር ለዘመናት ያልፈነቀለው ድንጋይ አልነበረም። “የትግራይ ሪፐብሊክ”፣ የቅኝ ገዥ እና ተገዥ የመሳሰሉ የተለያዩ ከፋፋይ የሐሰት ትርክቶችን በስፋት ሲገነባ የኖረ ቡድን ነው።
ዓላማውን ለማሳካትም ኢትዮጵያውያን ወንድም እኅቶቹን “ቅኝ ገዢ” ብሎ በመፈረጅ እና ታሪክን ለሴራው በሚመች መልኩ በማጣመም የጥላቻ መርዝን ሲዘራ ኖሯል።
አፈና፣ ደም አፋሳሽነት እና የሤራ ፖለቲካ የተጠናወተው የከሰረው የህወሓት ቡድን ፀረ አንድነት ብቻ ሳይሆን የገዛ ወንድሞቹን የሚበላ፣ ለራሱ ወዳጆችም የማይመለስ ርኅራኄ አልባ ቡድን ነው።
በ1969 ዓ.ም በድርጅቱ ውስጥ የተነሳውን ህንፍሽፍሽ መሠረት አድርጎ የገዛ ታጋዮቹን በጅምላ ረሽኗል። በሌላ ጊዜ ደግሞ የተለየ ሐሳብ ያነሱትን መሥራቾችን ሳይቀር “ጋንግሪን” በማለት አስወግዷል።
ይህ ቡድን ዜጎችን በማጎሪያ ካምፖቹ ውስጥ በማጎር አሰቃይቷል፣ በሰው ልጆች ላይ ሊፈጸሙ የማይገባቸውን አሰቃቂ ሰብዓዊ ወንጀሎችን ሲፈጽም ኖሯል።
ሌላው ታሪካዊ ክህደት በግገሓት ላይ የተፈጸመው ወንጀል ሲሆን፣ ይህም ሁለቱ ድርጅቶች አብረን እንታገል ብለው ተስማምተው አብረው ካደሩ በኋላ፣ የከሰረው የህወሓት ቡድን በሌሊት የግገሓት መሪዎችን በጥይት ደብድቦ የፈጁበት ታሪክ ነው።
ይህ ስብስብ ሀገር በመካድ በሕዝብ ስም እየነገደ የራሱን ቢዝነስ ኢምፓየር መገንባትን ዋነኛ ግቡ ያደረገ ቡድን ነው። አንጋፋው የቡድኑ መሥራች አቶ ገብሩ አስራት ዛሬ በጸጸት እንደሚመሰክሩት፣ የከሰረው የህወሓት ቡድን የኤርትራን ጉዳይ “የቅኝ ግዛት ነፃነት ጥያቄ ነው” በሚል የተሳሳተ ትርክት ተሟግቶ ኢትዮጵያን ያለ ባሕር በር አስቀርቷል።
ዛሬም ቢሆን ለትግራይ ሕዝብ አንዳች ነገር የማይፈይደው ይህ የከሰረ ቡድን፣ ሕዝቡን ከግጭት ወደ ትርምስ እያሸጋገረ፣ ከአጎራባች ሕዝቦች ጋር እያጋጨ የትግራይን ወጣት እያስጨረሰው ይገኛል። ሕዝቡን መላልሶ ለማያልቅ ስጋት፣ ውጥረት እና ችግር እየዳረገው ነው።
አሁን ግን፣ ከግማሽ ክፍለ ዘመን በላይ የዘለቀው ይህ የጥላቻ እና የክፋት ጉዞ ማብቂያው ደርሷል! የትግራይ ሕዝብ የቡድኑን ማፊያዊ ባሕርይ ጠንቅቆ ተረድቶ "በቃኝ!" ብሏል።
ቡድኑ የሕዝቡን ድምጽ ለማፈን እና "እኔ ነኝ የማውቅልህ" ለማለት ቢሞክርም፣ የዚህ አውዳሚ ኃይል መጨረሻው እጅግ ቀርቧል። አሁን ሕዝቡ ይህን የጥፋት ቡድን ከራሱ ነጥሎ የሚጥልበት ጊዜ ላይ ደርሰናል።
ዛሬ ለትግራይ ሕዝብ አዲስ ዘመን ሊበሰር ዋዜማው ላይ ነን። የትግራይ ወጣት ተስፋው የሚቀየርበት፣ ከጥላቻ ፖለቲካ ተላቅቆ ከሌላው ኢትዮጵያዊ ወንድሙ ጋር እጅ ለእጅ ተያይዞ የኢትዮጵያን የጋራ ብልጽግና የሚያረጋግጥበት ብሩህ ዘመን እጅግ ቅርብ ነው!
#ethiopia #tigray #peace
*********************
የከሰረው የህወሓት ቡድን ከተፈጠረበት ዘመን አንሥቶ እስካሁን ድረስ የሚናገረው ሌላ፣ የሚያደርገው ሌላ የሆነ የተቃርኖ ፖለቲካ ቁንጮ ነው።
ብዙ ጊዜ በጽሑፍ ማንነቱን ሲገልጽ የነበረ ቢሆንም፣ ይህ ስብስብ በእውነተኛ ትርጉሙ የፖለቲካ ፓርቲ ወይም የሀገር መሪ ሆኖ አያውቅም። ይልቁንም ላለፉት አምስት ዐሥርት ዓመታት፣ ክልልንም ሆነ ሀገርን ጨምድዶ በመያዝ እንደ አንድ የሽፍታ ቡድን የሚያስብ፣ በጥቂት ቤተሰቦች የጥቅም ትሥሥር የሚዘወር ማፍያዊ ስብስብ ነው።
ድሮም ሆነ አሁን ለፍላጎቱ ያልተገዙትን የሚጨቁን፣ ትብብርን የሚጠላ፣ የሚያጠፋ፣ የሚበትን እና የሚገድል፤ የጥላቻ ቁንጮ የሆነ፣ ፀረ አንድነት እና ፀረ ኅብረ ብሔራዊነት የተጠናወተው ቡድን ነው። ይህ ቡድን በ1968 ዓ.ም ባወጣው ማኒፌስቶው እውነተኛ ፀረ ሕዝብ ማንነቱን አሳይቷል።
የኢትዮጵያ ታሪክ ዋልታ የሆነውን፣ የጠንካራ ኢትዮጵያዊነት መሠረት የሆነውን የትግራይን ሕዝብ ከኢትዮጵያ ነጥሎ ለማኖር ለዘመናት ያልፈነቀለው ድንጋይ አልነበረም። “የትግራይ ሪፐብሊክ”፣ የቅኝ ገዥ እና ተገዥ የመሳሰሉ የተለያዩ ከፋፋይ የሐሰት ትርክቶችን በስፋት ሲገነባ የኖረ ቡድን ነው።
ዓላማውን ለማሳካትም ኢትዮጵያውያን ወንድም እኅቶቹን “ቅኝ ገዢ” ብሎ በመፈረጅ እና ታሪክን ለሴራው በሚመች መልኩ በማጣመም የጥላቻ መርዝን ሲዘራ ኖሯል።
አፈና፣ ደም አፋሳሽነት እና የሤራ ፖለቲካ የተጠናወተው የከሰረው የህወሓት ቡድን ፀረ አንድነት ብቻ ሳይሆን የገዛ ወንድሞቹን የሚበላ፣ ለራሱ ወዳጆችም የማይመለስ ርኅራኄ አልባ ቡድን ነው።
በ1969 ዓ.ም በድርጅቱ ውስጥ የተነሳውን ህንፍሽፍሽ መሠረት አድርጎ የገዛ ታጋዮቹን በጅምላ ረሽኗል። በሌላ ጊዜ ደግሞ የተለየ ሐሳብ ያነሱትን መሥራቾችን ሳይቀር “ጋንግሪን” በማለት አስወግዷል።
ይህ ቡድን ዜጎችን በማጎሪያ ካምፖቹ ውስጥ በማጎር አሰቃይቷል፣ በሰው ልጆች ላይ ሊፈጸሙ የማይገባቸውን አሰቃቂ ሰብዓዊ ወንጀሎችን ሲፈጽም ኖሯል።
ሌላው ታሪካዊ ክህደት በግገሓት ላይ የተፈጸመው ወንጀል ሲሆን፣ ይህም ሁለቱ ድርጅቶች አብረን እንታገል ብለው ተስማምተው አብረው ካደሩ በኋላ፣ የከሰረው የህወሓት ቡድን በሌሊት የግገሓት መሪዎችን በጥይት ደብድቦ የፈጁበት ታሪክ ነው።
ይህ ስብስብ ሀገር በመካድ በሕዝብ ስም እየነገደ የራሱን ቢዝነስ ኢምፓየር መገንባትን ዋነኛ ግቡ ያደረገ ቡድን ነው። አንጋፋው የቡድኑ መሥራች አቶ ገብሩ አስራት ዛሬ በጸጸት እንደሚመሰክሩት፣ የከሰረው የህወሓት ቡድን የኤርትራን ጉዳይ “የቅኝ ግዛት ነፃነት ጥያቄ ነው” በሚል የተሳሳተ ትርክት ተሟግቶ ኢትዮጵያን ያለ ባሕር በር አስቀርቷል።
ዛሬም ቢሆን ለትግራይ ሕዝብ አንዳች ነገር የማይፈይደው ይህ የከሰረ ቡድን፣ ሕዝቡን ከግጭት ወደ ትርምስ እያሸጋገረ፣ ከአጎራባች ሕዝቦች ጋር እያጋጨ የትግራይን ወጣት እያስጨረሰው ይገኛል። ሕዝቡን መላልሶ ለማያልቅ ስጋት፣ ውጥረት እና ችግር እየዳረገው ነው።
አሁን ግን፣ ከግማሽ ክፍለ ዘመን በላይ የዘለቀው ይህ የጥላቻ እና የክፋት ጉዞ ማብቂያው ደርሷል! የትግራይ ሕዝብ የቡድኑን ማፊያዊ ባሕርይ ጠንቅቆ ተረድቶ "በቃኝ!" ብሏል።
ቡድኑ የሕዝቡን ድምጽ ለማፈን እና "እኔ ነኝ የማውቅልህ" ለማለት ቢሞክርም፣ የዚህ አውዳሚ ኃይል መጨረሻው እጅግ ቀርቧል። አሁን ሕዝቡ ይህን የጥፋት ቡድን ከራሱ ነጥሎ የሚጥልበት ጊዜ ላይ ደርሰናል።
ዛሬ ለትግራይ ሕዝብ አዲስ ዘመን ሊበሰር ዋዜማው ላይ ነን። የትግራይ ወጣት ተስፋው የሚቀየርበት፣ ከጥላቻ ፖለቲካ ተላቅቆ ከሌላው ኢትዮጵያዊ ወንድሙ ጋር እጅ ለእጅ ተያይዞ የኢትዮጵያን የጋራ ብልጽግና የሚያረጋግጥበት ብሩህ ዘመን እጅግ ቅርብ ነው!
#ethiopia #tigray #peace
13 hours ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ የጉምሩክ ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር የሆኑትን አቶ አዘዘው ጫኔን በቁጥጥር ስር ማዋሉን አስታወቀ። ዜናው የሀገሪቱን የፋይናንስ እና የጸጥታ ተቋማት በእጅጉ ያስገረመ ሲሆን፣ ምክትል ኮሚሽነሩ በቁጥጥር ስር የዋሉት "ህገ-ወጥ ንግድን እና የኮንትሮባንድ ዝውውርን ይቆጣጠራሉ" ተብሎ በተሰጣቸው ከፍተኛ የኃላፊነት ወንበር ላይ ተቀምጠው፣ በተቃራኒው መንግስትን ለከፍተኛ ኪሳራ የዳረገ የተደራጀ ወንጀል ፈጽመዋል በሚል ነው።
አቶ አዘዘው ጫኔ የጉምሩክ ኮሚሽን የህግ ተገዥነት ዘርፍ ምክትል ኮሚሽነር ሆነው ሲያገለግሉ የቆዩ ቢሆንም፣ አሁን ላይ ግን ሀገርን ከኢኮኖሚ አሻጥር ከመጠበቅ ይልቅ አሻጥሩን በዋናነት ሲመሩት እንደነበር ፖሊስ አስታውቋል። ዘ-ሐበሻ የተመለከተው በምክትል ኮሚሽነሩ ላይ ከቀረቡት ዋና ዋና የጥርጣሬ ክሶች መካከል በገቢዎች እና ጉምሩክ አስተዳደር ውስጥ የዘረጉትን ሰፊ መረብ በመጠቀም፣ ትክክለኛ የግብር ምዘናዎችን በማዛባት እና መንግስት ማግኘት የነበረበትን ከፍተኛ ገቢ በማሳጣት የግብር ምዘና ማጭበርበር ወንጀል መፈጸማቸው በዋናነት ይጠቀሳል። ከዚህም በተጨማሪ የሐሰት የክፍያ ደረሰኞችን እና ህገ-ወጥ ሰነዶችን ወደ ተቋሙ ስርዓት በማስገባት እና በማስተናገድ የሰነድ ማጭበርበር እንደፈጸሙ ተገልጿል።
በተያያዘም የመንግሥትን ገቢ ለመቀነስ፣ የፈጸሙትን ወንጀል ዱካ ለማጥፋት እና ምርመራን ለማደናቀፍ ሲባል የተቋሙን ቁልፍ የኮምፒውተር መረጃዎች ሆን ብሎ በመደምሰስ የኤሌክትሮኒክስ መረጃዎችን በማጥፋት ክስ ቀርቦባቸዋል። ከዚህ ሁሉ ባለፈ፣ አሁን ላይ ሀገሪቱ ተግባራዊ እያደረገች ያለውን የማክሮ-ኢኮኖሚ ማሻሻያ ፕሮግራም ለማስተጓጎል በማሰብ፣ ከኮንትሮባንድ አዘዋዋሪዎች እና ከሌሎች ህገ-ወጥ የጥቅም መረቦች ጋር በቀጥታ በመመሳጠር የተደራጀ የኢኮኖሚ አሻጥር መፈጸማቸው በምርመራ መመላከቱን ፖሊስ አብራርቷል።
ይህ ክስተት የህግ የበላይነትን እና የተቋማት ታማኝነትን በተመለከተ ትልቅ ጥያቄ የሚያስነሳ ነው። የህግ ተገዥነትን እንዲያስከብሩ የተሾሙ ከፍተኛ ባለስልጣን፣ የመንግስትን የኤሌክትሮኒክስ መረጃዎች እስከማጥፋት እና ከኮንትሮባንዲስቶች ጋር እስከመመሳጠር መድረሳቸው በጉምሩክ ኮሚሽኑ የውስጥ ቁጥጥር ስርዓት ላይ ትልቅ የደህንነት ክፍተት መኖሩን ፍንትው አድርጎ ያሳያል።
በተለይም መንግስት የማክሮ-ኢኮኖሚ ማሻሻያውን ተከትሎ የውጭ ምንዛሬ እና የገበያ መረጋጋትን ለማምጣት በሚጥርበት በዚህ ወሳኝ ወቅት፣ ቁልፍ የተቋሙ አመራሮች ራሳቸው ስርዓቱን ለማፍረስ በሚደረግ አሻጥር ውስጥ መገኘታቸው፣ የጸረ-ሙስና ዘመቻው ከመቼውም ጊዜ በላይ ከራሱ ከመንግስት መዋቅር መጀመር እንዳለበት የሚያመላክት ነው። ፌዴራል ፖሊስ በጉዳዩ ላይ የጀመረውን ጥልቅ ምርመራ አጠናክሮ መቀጠሉን ገልጿል።
አቶ አዘዘው ጫኔ የጉምሩክ ኮሚሽን የህግ ተገዥነት ዘርፍ ምክትል ኮሚሽነር ሆነው ሲያገለግሉ የቆዩ ቢሆንም፣ አሁን ላይ ግን ሀገርን ከኢኮኖሚ አሻጥር ከመጠበቅ ይልቅ አሻጥሩን በዋናነት ሲመሩት እንደነበር ፖሊስ አስታውቋል። ዘ-ሐበሻ የተመለከተው በምክትል ኮሚሽነሩ ላይ ከቀረቡት ዋና ዋና የጥርጣሬ ክሶች መካከል በገቢዎች እና ጉምሩክ አስተዳደር ውስጥ የዘረጉትን ሰፊ መረብ በመጠቀም፣ ትክክለኛ የግብር ምዘናዎችን በማዛባት እና መንግስት ማግኘት የነበረበትን ከፍተኛ ገቢ በማሳጣት የግብር ምዘና ማጭበርበር ወንጀል መፈጸማቸው በዋናነት ይጠቀሳል። ከዚህም በተጨማሪ የሐሰት የክፍያ ደረሰኞችን እና ህገ-ወጥ ሰነዶችን ወደ ተቋሙ ስርዓት በማስገባት እና በማስተናገድ የሰነድ ማጭበርበር እንደፈጸሙ ተገልጿል።
በተያያዘም የመንግሥትን ገቢ ለመቀነስ፣ የፈጸሙትን ወንጀል ዱካ ለማጥፋት እና ምርመራን ለማደናቀፍ ሲባል የተቋሙን ቁልፍ የኮምፒውተር መረጃዎች ሆን ብሎ በመደምሰስ የኤሌክትሮኒክስ መረጃዎችን በማጥፋት ክስ ቀርቦባቸዋል። ከዚህ ሁሉ ባለፈ፣ አሁን ላይ ሀገሪቱ ተግባራዊ እያደረገች ያለውን የማክሮ-ኢኮኖሚ ማሻሻያ ፕሮግራም ለማስተጓጎል በማሰብ፣ ከኮንትሮባንድ አዘዋዋሪዎች እና ከሌሎች ህገ-ወጥ የጥቅም መረቦች ጋር በቀጥታ በመመሳጠር የተደራጀ የኢኮኖሚ አሻጥር መፈጸማቸው በምርመራ መመላከቱን ፖሊስ አብራርቷል።
ይህ ክስተት የህግ የበላይነትን እና የተቋማት ታማኝነትን በተመለከተ ትልቅ ጥያቄ የሚያስነሳ ነው። የህግ ተገዥነትን እንዲያስከብሩ የተሾሙ ከፍተኛ ባለስልጣን፣ የመንግስትን የኤሌክትሮኒክስ መረጃዎች እስከማጥፋት እና ከኮንትሮባንዲስቶች ጋር እስከመመሳጠር መድረሳቸው በጉምሩክ ኮሚሽኑ የውስጥ ቁጥጥር ስርዓት ላይ ትልቅ የደህንነት ክፍተት መኖሩን ፍንትው አድርጎ ያሳያል።
በተለይም መንግስት የማክሮ-ኢኮኖሚ ማሻሻያውን ተከትሎ የውጭ ምንዛሬ እና የገበያ መረጋጋትን ለማምጣት በሚጥርበት በዚህ ወሳኝ ወቅት፣ ቁልፍ የተቋሙ አመራሮች ራሳቸው ስርዓቱን ለማፍረስ በሚደረግ አሻጥር ውስጥ መገኘታቸው፣ የጸረ-ሙስና ዘመቻው ከመቼውም ጊዜ በላይ ከራሱ ከመንግስት መዋቅር መጀመር እንዳለበት የሚያመላክት ነው። ፌዴራል ፖሊስ በጉዳዩ ላይ የጀመረውን ጥልቅ ምርመራ አጠናክሮ መቀጠሉን ገልጿል።
15 hours ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ በሥራ እና ክህሎት ሚኒስቴር ከፍተኛ ባለስልጣናት ላይ ከተመሰረተው የሙስና ክስ መዝገብ ጋር በተያያዘ በቁጥጥር ስር የዋለችውን የወ/ት ኢክራም አማን ገቲሶን ፎቶግራፍ ዛሬ በይፋ አውጥቷል። ዘ-ሐበሻ ከዚህ ቀደም ግለሰቧ በቁጥጥር ስር መዋሏን በዘገበበት ወቅት ፎቶዋን ማግኘት እንዳልቻለ መግለጹ የሚታወስ ሲሆን፣ ዛሬ ግን ፖሊስ ከሌሎች ተከሳሽ ባለስልጣናት ፎቶዎች ጋር አብሮ ይፋ አድርጎታል።
ወ/ት ኢክራም በሙስና መዝገቡ ላይ በዋነኝነት የተጠቀሰችው የተከሳሹ የአቶ ነቢል አንዋር የቅርብ ሰው በመሆን ነው። በክሱ እንደተመላከተው፣ ግለሰቧ ለአቶ ብርሃኑ አለቃ፣ ለአቶ ኤርሚያስ ተክሉ እና ለአቶ ነቢል አንዋር ከተለያዩ አካላት የሚሰበሰበውን የሙስና ገንዘብ በመቀበል ለአቶ ነቢል ገቢ ስታደርግ ቆይታለች።
በተጨማሪም ኤጀንሲዎችን በመክፈትና በመዝጋት ሂደት፣ እንዲሁም በሌሎች ተያያዥ ጉዳዮች ላይ በኤጀንሲዎች እና በ'ELMIS' ሠራተኞች መካከል እንደ ደላላ በመሆን ከፍተኛ የገንዘብ ጥቅም ስታገኝ እንደነበር ተገልጿል።
በዚህ ህገ-ወጥ የደላላነት እና የገንዘብ ማሰባሰብ ተግባሯ፣ ወ/ት ኢክራም በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና በአዋሽ ባንክ በከፈተቻቸው ሶስት የተለያዩ የባንክ ሂሳቦች ውስጥ በአጠቃላይ 30,840,490.99 (ሰላሳ ሚሊዮን ስምንት መቶ አርባ ሺህ አራት መቶ ዘጠና ብር ከዘጠና ዘጠኝ ሳንቲም) ገቢ እንደተደረገላት የምርመራ መዝገቡ ያሳያል።
በዚሁ ከባድ የሙስና ወንጀል ጥቆማ መሰረት፣ ተጠርጣሪዋ ሐምሌ 17 ቀን 2018 ዓ.ም. (17/11/2018 ዓ.ም) በፖሊስ ቁጥጥር ስር ውላ ምርመራ እየተደረገባት መሆኑን በዘ-ሐበሻ ዜና ከዚህ ቀደም መዘገባችን ይታወሳል።
ወ/ት ኢክራም በሙስና መዝገቡ ላይ በዋነኝነት የተጠቀሰችው የተከሳሹ የአቶ ነቢል አንዋር የቅርብ ሰው በመሆን ነው። በክሱ እንደተመላከተው፣ ግለሰቧ ለአቶ ብርሃኑ አለቃ፣ ለአቶ ኤርሚያስ ተክሉ እና ለአቶ ነቢል አንዋር ከተለያዩ አካላት የሚሰበሰበውን የሙስና ገንዘብ በመቀበል ለአቶ ነቢል ገቢ ስታደርግ ቆይታለች።
በተጨማሪም ኤጀንሲዎችን በመክፈትና በመዝጋት ሂደት፣ እንዲሁም በሌሎች ተያያዥ ጉዳዮች ላይ በኤጀንሲዎች እና በ'ELMIS' ሠራተኞች መካከል እንደ ደላላ በመሆን ከፍተኛ የገንዘብ ጥቅም ስታገኝ እንደነበር ተገልጿል።
በዚህ ህገ-ወጥ የደላላነት እና የገንዘብ ማሰባሰብ ተግባሯ፣ ወ/ት ኢክራም በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና በአዋሽ ባንክ በከፈተቻቸው ሶስት የተለያዩ የባንክ ሂሳቦች ውስጥ በአጠቃላይ 30,840,490.99 (ሰላሳ ሚሊዮን ስምንት መቶ አርባ ሺህ አራት መቶ ዘጠና ብር ከዘጠና ዘጠኝ ሳንቲም) ገቢ እንደተደረገላት የምርመራ መዝገቡ ያሳያል።
በዚሁ ከባድ የሙስና ወንጀል ጥቆማ መሰረት፣ ተጠርጣሪዋ ሐምሌ 17 ቀን 2018 ዓ.ም. (17/11/2018 ዓ.ም) በፖሊስ ቁጥጥር ስር ውላ ምርመራ እየተደረገባት መሆኑን በዘ-ሐበሻ ዜና ከዚህ ቀደም መዘገባችን ይታወሳል።
18 hours ago
የኢትዮጵያና ስሪላንካ ወዳጅነት በኪነ-ጥበብ እና በወጣቶች ትብብር ሊያበብ ነው
#ethiopia | በኢትዮጵያ የስሪላንካ አምባሳደር ኒርማላ ኢንዱማቲ ዲያስ ፓራናቪታና ከኢትዮጵያ የኪነ-ጥበብ እና የትወና ዘርፍ ተወካዮች ጋር ያደረጉትን ውይይት ተከትሎ የሁለቱን ሀገራት ወዳጅነት በባህል ዲፕሎማሲ፣ በወጣቶች አቅም ግንባታ እና በደቡብ-ደቡብ ትብብር ለማጠናከር ያለመ እንቅስቃሴ ጀምረዋል።
አምባሳደሯ ከአምሳ ሦስት በላይ የሰርከስ ትምህርት ቤቶችን ከሚወክለው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ሰርከስ ማህበራት ጥምረት (ENCAC) ፕሬዝዳንት አቶ ተክሉ አሻግሬ (ሄኖክ) ፣ ከ"ቢዮንድ ዳንስ ስቱዲዮ" የደንበኞች አገልግሎት ማኔጀር ሲና አምሳሉ እንዲሁም ከፍካት ሰርከስ አሰልጣኝና ቡድን መሪ አቶ ተመሰገን ግርማ ጋር ተከታታይ ውይይቶችን አድርገዋል።
በውይይቱ ወቅት አምባሳደሯ የስሪላንካን ውብ የባህል ቅርስ በማስተዋወቅ የኢትዮጵያ ወጣት ከዋክብት በባህላዊ ውዝዋዜ፣ በቪዲዮ ትምህርቶች፣ በጉብኝቶች እና በባህል ፌስቲቫሎች የሚሳተፉበትን "ሪትም ኦፍ ላንካ" (Rhythm of Lanka) የተሰኘ መርሃ ግብር አስተዋውቀዋል።
በተጨማሪም በሰርከስና በውዝዋዜ ጥበብ ለተሰማሩ ወጣቶች የጋራ መድረኮችን በመፍጠር በዓለም አቀፍ ደረጃ አቅማቸውን የሚያሳዩበትና ተሞክሮ የሚለዋወጡበት ዕድል እንደሚመቻች ተገልጿል።
የድርጅቶቹ ተወካዮችም የተጀመረውን የትብብር ጥሪ በበጎ የተቀበሉት ሲሆን መርሃ ግብሩ የወጣቶችን አቅም ከማሳደግ ባለፈ የሁለቱን ሀገራት ታሪካዊና ባህላዊ ትስስር ወደ ላቀ ደረጃ እንደሚያሸጋግረው ተገልጿል።
በያፌት ገ/ህይወት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#ethiopia | በኢትዮጵያ የስሪላንካ አምባሳደር ኒርማላ ኢንዱማቲ ዲያስ ፓራናቪታና ከኢትዮጵያ የኪነ-ጥበብ እና የትወና ዘርፍ ተወካዮች ጋር ያደረጉትን ውይይት ተከትሎ የሁለቱን ሀገራት ወዳጅነት በባህል ዲፕሎማሲ፣ በወጣቶች አቅም ግንባታ እና በደቡብ-ደቡብ ትብብር ለማጠናከር ያለመ እንቅስቃሴ ጀምረዋል።
አምባሳደሯ ከአምሳ ሦስት በላይ የሰርከስ ትምህርት ቤቶችን ከሚወክለው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ሰርከስ ማህበራት ጥምረት (ENCAC) ፕሬዝዳንት አቶ ተክሉ አሻግሬ (ሄኖክ) ፣ ከ"ቢዮንድ ዳንስ ስቱዲዮ" የደንበኞች አገልግሎት ማኔጀር ሲና አምሳሉ እንዲሁም ከፍካት ሰርከስ አሰልጣኝና ቡድን መሪ አቶ ተመሰገን ግርማ ጋር ተከታታይ ውይይቶችን አድርገዋል።
በውይይቱ ወቅት አምባሳደሯ የስሪላንካን ውብ የባህል ቅርስ በማስተዋወቅ የኢትዮጵያ ወጣት ከዋክብት በባህላዊ ውዝዋዜ፣ በቪዲዮ ትምህርቶች፣ በጉብኝቶች እና በባህል ፌስቲቫሎች የሚሳተፉበትን "ሪትም ኦፍ ላንካ" (Rhythm of Lanka) የተሰኘ መርሃ ግብር አስተዋውቀዋል።
በተጨማሪም በሰርከስና በውዝዋዜ ጥበብ ለተሰማሩ ወጣቶች የጋራ መድረኮችን በመፍጠር በዓለም አቀፍ ደረጃ አቅማቸውን የሚያሳዩበትና ተሞክሮ የሚለዋወጡበት ዕድል እንደሚመቻች ተገልጿል።
የድርጅቶቹ ተወካዮችም የተጀመረውን የትብብር ጥሪ በበጎ የተቀበሉት ሲሆን መርሃ ግብሩ የወጣቶችን አቅም ከማሳደግ ባለፈ የሁለቱን ሀገራት ታሪካዊና ባህላዊ ትስስር ወደ ላቀ ደረጃ እንደሚያሸጋግረው ተገልጿል።
በያፌት ገ/ህይወት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
21 hours ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) — በኢንተር ኮንቲኔንታል ሆቴል በተካሄደ ልዩ የዕውቅና እና የሽኝት ሥነ-ሥርዓት ላይ እንደተገለጸው፣ ጸደይ ባንክ አዲሱን ዋና ሥራ አስፈጻሚ ዶ/ር ዮሐንስ አያሌውን ከተቀበለ በኋላ የፋይናንስ እና የአሰራር ለውጦችን ማስመዝገብ መቻሉን ገለጸ። ባንኩ ከዚህ ቀደም በተደጋጋሚ ይገጥመው የነበረውን የኪሳራ ታሪክ በመቀልበስ፣ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት 4.3 ቢሊዮን ብር የተጣራ ትርፍ ማግኘት መቻሉ ተገልጿል።
በባንክ ኢንዱስትሪው ትልቅ ማነቆ የሆነውን የተበላሸ ብድር (Non-Performing Loans - NPL) መጠን በመቀነስ ረገድ ጸደይ ባንክ የተሻለ ውጤት እንዳስመዘገብም ተነግሯል። ባለፈው በጀት ዓመት ከፍተኛ አደጋ በሚያመለክተው የ21 በመቶ ደረጃ ላይ የነበረው የተበላሸ ብድር ምጣኔ፣ በስድስት ወራት ውስጥ ወደ 6 በመቶ ዝቅ ብሎ የነበረ ሲሆን፤ አሁን በጀት ዓመቱ ሲጠናቀቅ ደግሞ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ካስቀመጠው አስገዳጅ የ5 በመቶ ጣሪያ በታች ማውረድ መቻሉ ተብራርቷል። ይህ ስኬት አዲሱ አመራር የብድር አመላለስ ሥርዓቱን ውጤታማ እና ጥብቅ በሆነ መንገድ በማሻሻሉ ነው ተብሏል።
በሥነ-ሥርዓቱ ላይ የባንኩን አጠቃላይ ግብ እና የሥራ ዕቅድ በማሳካት የላቀ ውጤት ላመጡ የሥራ ኃላፊዎች የሽልማት አሰጣጥ ፕሮግራም ተካሂዷል። ከእነዚህም መካከል የፍኖተሰላም ዲስትሪክት ማናጀር የሆኑት አቶ ደሳለኝ ወንዳለ ተጠቃሽ ናቸው። አቶ ደሳለኝ በሁሉም ቁልፍ የአፈጻጸም መለኪያዎች (KPIs) ባስመዘገቡት አመርቂ ውጤት ልዩ ተሸላሚ መሆን ችለዋል።
በዕለቱ የቀድሞው ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ መኮንን የለውወሰንም የሽኝት ፕሮግራም ተዘጋጅቶላቸዋል። ለባንኩ ባለፉት 30 ዓመታት አበረከቱት ለተባለው አገልግሎት "ዕውቅና ለመስጠት" ቶዮታ RAV4 Hybrid 2026 ሞዴል መኪና ሽልማት የተበረከተላቸው ሲሆን፣ ሌሎች ጥቅማጥቅሞችም ሙሉ በሙሉ እንዲከበሩላቸው መደረጉን ለዘ-ሐበሻ የደረሱ የውስጥ መረጃዎች ጠቁመዋል።
ባንኩ በዚሁ መድረክ ላይ የረዥም ጊዜ የስትራቴጂክ ዕቅዱን እና ራዕዩንም ይፋ አድርጓል። በዚህም መሠረት የባንኩ ቀጣይ ትልልቅ ግቦቼ የሚከተሉት ናቸው ብሏል፦
በአውሮፓውያኑ 2030 በኢትዮጵያ ውስጥ ከሚገኙ ግዙፍ 4 የንግድ ባንኮች አንዱ መሆን።
በአውሮፓውያኑ 2040 ደግሞ የሀገር ውስጥ ገበያን አልፎ በመላው አፍሪካ ከሚገኙ 40 ምርጥ የንግድ ባንኮች ተርታ መሰለፍ።
በባንክ ኢንዱስትሪው ትልቅ ማነቆ የሆነውን የተበላሸ ብድር (Non-Performing Loans - NPL) መጠን በመቀነስ ረገድ ጸደይ ባንክ የተሻለ ውጤት እንዳስመዘገብም ተነግሯል። ባለፈው በጀት ዓመት ከፍተኛ አደጋ በሚያመለክተው የ21 በመቶ ደረጃ ላይ የነበረው የተበላሸ ብድር ምጣኔ፣ በስድስት ወራት ውስጥ ወደ 6 በመቶ ዝቅ ብሎ የነበረ ሲሆን፤ አሁን በጀት ዓመቱ ሲጠናቀቅ ደግሞ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ካስቀመጠው አስገዳጅ የ5 በመቶ ጣሪያ በታች ማውረድ መቻሉ ተብራርቷል። ይህ ስኬት አዲሱ አመራር የብድር አመላለስ ሥርዓቱን ውጤታማ እና ጥብቅ በሆነ መንገድ በማሻሻሉ ነው ተብሏል።
በሥነ-ሥርዓቱ ላይ የባንኩን አጠቃላይ ግብ እና የሥራ ዕቅድ በማሳካት የላቀ ውጤት ላመጡ የሥራ ኃላፊዎች የሽልማት አሰጣጥ ፕሮግራም ተካሂዷል። ከእነዚህም መካከል የፍኖተሰላም ዲስትሪክት ማናጀር የሆኑት አቶ ደሳለኝ ወንዳለ ተጠቃሽ ናቸው። አቶ ደሳለኝ በሁሉም ቁልፍ የአፈጻጸም መለኪያዎች (KPIs) ባስመዘገቡት አመርቂ ውጤት ልዩ ተሸላሚ መሆን ችለዋል።
በዕለቱ የቀድሞው ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ መኮንን የለውወሰንም የሽኝት ፕሮግራም ተዘጋጅቶላቸዋል። ለባንኩ ባለፉት 30 ዓመታት አበረከቱት ለተባለው አገልግሎት "ዕውቅና ለመስጠት" ቶዮታ RAV4 Hybrid 2026 ሞዴል መኪና ሽልማት የተበረከተላቸው ሲሆን፣ ሌሎች ጥቅማጥቅሞችም ሙሉ በሙሉ እንዲከበሩላቸው መደረጉን ለዘ-ሐበሻ የደረሱ የውስጥ መረጃዎች ጠቁመዋል።
ባንኩ በዚሁ መድረክ ላይ የረዥም ጊዜ የስትራቴጂክ ዕቅዱን እና ራዕዩንም ይፋ አድርጓል። በዚህም መሠረት የባንኩ ቀጣይ ትልልቅ ግቦቼ የሚከተሉት ናቸው ብሏል፦
በአውሮፓውያኑ 2030 በኢትዮጵያ ውስጥ ከሚገኙ ግዙፍ 4 የንግድ ባንኮች አንዱ መሆን።
በአውሮፓውያኑ 2040 ደግሞ የሀገር ውስጥ ገበያን አልፎ በመላው አፍሪካ ከሚገኙ 40 ምርጥ የንግድ ባንኮች ተርታ መሰለፍ።
Sponsored by
Surafel
2 days ago
የቀድሞው የኢትዮጵያ አየር መንገድ መሪ ተወልደ ገብረማሪያም የኤር ኢንዲያ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሆነው ተሾሙ
የሕንድ ሁለተኛው ትልቁ አየር መንገድ የቀድሞውን የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ሥራ አስፈፋሚ ተወልደ ወልደማሪያምን ዋና ሥራ አስፈጻሚው አድርጎ መሾሙን አስታወቀ።
የኢትዮጵያ አየር መንገድን ከአስር ዓመት በላይ የመሩት እና አየር መንገዱን ከአፍሪካ ግዙፉ እንዲሁም ቀዳሚው በማድረግ አሁን ከደረሰበት ደረጃ ላይ በማድረስ ቁልፍ ሚና የነበራቸው ተወልደ፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ያካሄደውን የባለ ብዙ ሚሊዮን ዶላር ማስፋፋት እና ባለ ብዙ አውሮፕላኖች ባለቤት እንዲሆን ያስቻሉ መሆናቸው ይነገራል።
አቶ ተወልደ ገብረማሪያም በኢትዮጵያ አየር መንገድ ስኬት ላይ ብቻ ሳይሆን ፈተናዎች በገጠሙት ጊዜ ተቋሙ ተግዳሮቶችን ተቋቁሞ በስኬት እንዲያልፍ አድርገዋል።
በተለይም በአየር መንገዱ ታሪክ ውስጥ ከባድ በነበሩት የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ወቅት በርካታ አየር መንገዶች ለኪሳራ እና ከሥራ ውጪ ለመሆን ሲገደዱ የኢትዮጵያ አየር መንገድ በሥራው ላይ ለውጥ በማድረግ ትርፋማ ለመሆን አስችለውታል።
በተጨማሪም ከአዲስ አበባ ወደ ናይሮቢ ሲበር ተከስክሶ ሁሉም መንገደኞች እና የአውሮፕላኑ ሠራተኞች ከሞቱበት የቦይን 737 ማክስ አውሮፕላን አደጋ ወቅት የአየር መንገዱን ጥንካሬ ዝና ጠብቀው ከቀውሱ ለመውጣት መቻላቸው ከሚጠቀሱላችው ስኬቶቻቸው መካከል ናቸው።
አቶ ተወልደ ገብረማሪያም አሁን የዋና ሥራ አስፈጻሚውን ቦታ የሚረከቡት ኤር ኢንዲያ አየር መንገድ ባለፈው የአውሮፓውያን ዓመት አውሮፕላኑ ተከስክሶ 260 መንገደኞች ከሞቱ በኋላ በከባድ ፈተና ውስጥ ይገኛል።
አየር መንገዱ በተጨማሪም ከፍተኛ የገንዘብ እና የሥራውን የማካሄድ ፈተና የገጠመው ሲሆን፣ ከደረሰበት አደጋ ተያይዞ በአቪየሽን ተቆጣጣሪ አካላት ጥብቅ ቁጥጥር የሚደረግበት ነው።
አቶ ተወልደ የመሪነት ኃላፊነቱን የሚረከቡት ኤር ኢንዲያ በሚያጓጉዛቸው መንገደኞች ብዛት በሕንድ ውስጥ ካሉ አየር መንገዶች ሁለተኛው ትልቁ አየር መንገድ ነው።
ታታ ግሩፕ 75 በመቶ የባለቤትንት ድርሻውን እንዲሁም የሴንጋፖር አየር መንገድ 25 ባለቤትነት ያለው ወደ 200 የሚጠጉ አውሮፕላኖች እና ከ31 ሺህ በላይ ሠራተኞች የሚሰስተደድረው አየር መንገዱ ወደ 90 ዓለም አቀፍ እና የአገር ውስጥ የበረራ መስመሮች አሉት።
በኢትዮጵያ አየር መንገድ ውስጥ ከ20 ዓመታት በላይ በተለያዩ ኃላፊነቶች ላይ የሠሩት አቶ ተወልደ ገብረማሪያም የአየር መንገዱ ዋና ሥራ አስፈጻሚ የሆኑት በጥር 2003 ዓ.ም. ነበረ።
አቶ ተወልደ በተባበሩት መንግሥታት ውስጥ ዘላቂነት ባለው ትራንስፖርት ዘርፍ ከፍተኛ የአማካሪዎች ቡድን አባል ሆነው ሠርተዋል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ አባል በሆነበት የስታር አሊያንስ ዋና የቦርድ አባል፣ የዓለም አቀፉ የትራንስፖርት ማኅበር (አይኤቲኤ) የቦርድ አባል በተጨማሪም የአፍሪካ የአየር መንገዶች ማኅበር (ኤኤፍአርኤኤ) የዋና ኮሚቴ አባል በመሆን አገልግለዋል።
አቶ ተወልደ የአፍሪካ የጉዞ ማኅበር (ኤቲኤ) የቦርድ አባል እና የኢትዮጵያ የቱሪዝም ድርጅት (ኢቲኦ) የዳይሬክተሮች ቦርድ አባልም ነበሩ።
አቶ ተወልደ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሆነው ባገለገሉባቸው በርካታ ዓመታት የተለያዩ ሽልማቶችን አግኝተዋል።
ከሽልማቶቹ መካከል የዓመቱ የአፍሪካ ምርጥ ዋና ሥራ አስፈጻሚ፣ ምርጥ የአፍሪካ የቢዝነስ መሪ፣ የቀጣናዊ የአየር መንገድ አመራር ሽልማት እንዲሁም ምርጥ ፆታን ያማከለ ሥራ አስፈፃሚ የሚሉት ይጠቀሳሉ።
የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ በኢኮኖሚክስ፣ ሁለተኛ ዲግሪያቸውን ከዩናይትድ ኪንግደም ኦፕን ዩኒቨርስቲ በንግድ አስተዳደር ያገኙ ሲሆን ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የክብር ዶክትሬትም ተበርክቶላቸዋል።
አቶ ተወልደ ገብረ ማሪያም ከአስር ዓመት በላይ በስኬት የመሩትን የኢትዮጵያ አየር መንገድን የለቀቁት በጤና ሁኔታን በምክንያት ጠቅሰው በ2014 ዓ.ም. ነበር።
BBC
የሕንድ ሁለተኛው ትልቁ አየር መንገድ የቀድሞውን የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ሥራ አስፈፋሚ ተወልደ ወልደማሪያምን ዋና ሥራ አስፈጻሚው አድርጎ መሾሙን አስታወቀ።
የኢትዮጵያ አየር መንገድን ከአስር ዓመት በላይ የመሩት እና አየር መንገዱን ከአፍሪካ ግዙፉ እንዲሁም ቀዳሚው በማድረግ አሁን ከደረሰበት ደረጃ ላይ በማድረስ ቁልፍ ሚና የነበራቸው ተወልደ፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ያካሄደውን የባለ ብዙ ሚሊዮን ዶላር ማስፋፋት እና ባለ ብዙ አውሮፕላኖች ባለቤት እንዲሆን ያስቻሉ መሆናቸው ይነገራል።
አቶ ተወልደ ገብረማሪያም በኢትዮጵያ አየር መንገድ ስኬት ላይ ብቻ ሳይሆን ፈተናዎች በገጠሙት ጊዜ ተቋሙ ተግዳሮቶችን ተቋቁሞ በስኬት እንዲያልፍ አድርገዋል።
በተለይም በአየር መንገዱ ታሪክ ውስጥ ከባድ በነበሩት የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ወቅት በርካታ አየር መንገዶች ለኪሳራ እና ከሥራ ውጪ ለመሆን ሲገደዱ የኢትዮጵያ አየር መንገድ በሥራው ላይ ለውጥ በማድረግ ትርፋማ ለመሆን አስችለውታል።
በተጨማሪም ከአዲስ አበባ ወደ ናይሮቢ ሲበር ተከስክሶ ሁሉም መንገደኞች እና የአውሮፕላኑ ሠራተኞች ከሞቱበት የቦይን 737 ማክስ አውሮፕላን አደጋ ወቅት የአየር መንገዱን ጥንካሬ ዝና ጠብቀው ከቀውሱ ለመውጣት መቻላቸው ከሚጠቀሱላችው ስኬቶቻቸው መካከል ናቸው።
አቶ ተወልደ ገብረማሪያም አሁን የዋና ሥራ አስፈጻሚውን ቦታ የሚረከቡት ኤር ኢንዲያ አየር መንገድ ባለፈው የአውሮፓውያን ዓመት አውሮፕላኑ ተከስክሶ 260 መንገደኞች ከሞቱ በኋላ በከባድ ፈተና ውስጥ ይገኛል።
አየር መንገዱ በተጨማሪም ከፍተኛ የገንዘብ እና የሥራውን የማካሄድ ፈተና የገጠመው ሲሆን፣ ከደረሰበት አደጋ ተያይዞ በአቪየሽን ተቆጣጣሪ አካላት ጥብቅ ቁጥጥር የሚደረግበት ነው።
አቶ ተወልደ የመሪነት ኃላፊነቱን የሚረከቡት ኤር ኢንዲያ በሚያጓጉዛቸው መንገደኞች ብዛት በሕንድ ውስጥ ካሉ አየር መንገዶች ሁለተኛው ትልቁ አየር መንገድ ነው።
ታታ ግሩፕ 75 በመቶ የባለቤትንት ድርሻውን እንዲሁም የሴንጋፖር አየር መንገድ 25 ባለቤትነት ያለው ወደ 200 የሚጠጉ አውሮፕላኖች እና ከ31 ሺህ በላይ ሠራተኞች የሚሰስተደድረው አየር መንገዱ ወደ 90 ዓለም አቀፍ እና የአገር ውስጥ የበረራ መስመሮች አሉት።
በኢትዮጵያ አየር መንገድ ውስጥ ከ20 ዓመታት በላይ በተለያዩ ኃላፊነቶች ላይ የሠሩት አቶ ተወልደ ገብረማሪያም የአየር መንገዱ ዋና ሥራ አስፈጻሚ የሆኑት በጥር 2003 ዓ.ም. ነበረ።
አቶ ተወልደ በተባበሩት መንግሥታት ውስጥ ዘላቂነት ባለው ትራንስፖርት ዘርፍ ከፍተኛ የአማካሪዎች ቡድን አባል ሆነው ሠርተዋል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ አባል በሆነበት የስታር አሊያንስ ዋና የቦርድ አባል፣ የዓለም አቀፉ የትራንስፖርት ማኅበር (አይኤቲኤ) የቦርድ አባል በተጨማሪም የአፍሪካ የአየር መንገዶች ማኅበር (ኤኤፍአርኤኤ) የዋና ኮሚቴ አባል በመሆን አገልግለዋል።
አቶ ተወልደ የአፍሪካ የጉዞ ማኅበር (ኤቲኤ) የቦርድ አባል እና የኢትዮጵያ የቱሪዝም ድርጅት (ኢቲኦ) የዳይሬክተሮች ቦርድ አባልም ነበሩ።
አቶ ተወልደ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሆነው ባገለገሉባቸው በርካታ ዓመታት የተለያዩ ሽልማቶችን አግኝተዋል።
ከሽልማቶቹ መካከል የዓመቱ የአፍሪካ ምርጥ ዋና ሥራ አስፈጻሚ፣ ምርጥ የአፍሪካ የቢዝነስ መሪ፣ የቀጣናዊ የአየር መንገድ አመራር ሽልማት እንዲሁም ምርጥ ፆታን ያማከለ ሥራ አስፈፃሚ የሚሉት ይጠቀሳሉ።
የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ በኢኮኖሚክስ፣ ሁለተኛ ዲግሪያቸውን ከዩናይትድ ኪንግደም ኦፕን ዩኒቨርስቲ በንግድ አስተዳደር ያገኙ ሲሆን ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የክብር ዶክትሬትም ተበርክቶላቸዋል።
አቶ ተወልደ ገብረ ማሪያም ከአስር ዓመት በላይ በስኬት የመሩትን የኢትዮጵያ አየር መንገድን የለቀቁት በጤና ሁኔታን በምክንያት ጠቅሰው በ2014 ዓ.ም. ነበር።
BBC
2 days ago
(ዘ-ሐበሻ ሕይወት) ሞት የሰው ልጅ የጋራ እጣ ፈንታ ቢሆንም፣ የህይወት አጋርን እና የልብ ወዳጅን ማጣት የሚያሳድረው ሀዘን እጅግ ጥልቅ እና ከባድ ነው። በኢትዮጵያ የሙዚቃ መድረክ ላይ ለረጅም ዓመታት በጣፋጭ ድምጿ እና በማይጠገቡ ስራዎቿ የብዙዎችን ልብ ስታስደስት የኖረችው ተወዳጇ ድምፃዊት ገነት ማስረሻ፣ የህይወት አጋሯን እና የልጆቿን አባት አቶ አዱኛ ይስማቸውን በሞት ተነጥቃለች።
አቶ አዱኛ ይስማቸው የልጅነት አየራቸውን በተነፈሱባት እና በተወለዱባት ታሪካዊቷ የጎንደር ምድር፣ ልዩ ስሟ እንፍራዝ በተባለችው ውብ ከተማ በ1948 ዓ.ም ነበር ወደዚህ ዓለም የመጡት። በምድራዊ የህይወት ጉዟቸውም በውጣ ውረድ ውስጥ አልፈው 70 የተከበሩ ዓመታትን አስቆጥረዋል።
ድምፃዊት ገነት እና አቶ አዱኛ በፍቅር እና በመከባበር የታነፀ ፅኑ ትዳርን መስርተው፣ የትዳራቸው የፍቅር ማሳያ የሆኑ ሁለት ወንድ እና ሁለት ሴት ልጆችን አፍርተዋል። አቶ አዱኛ ለድምፃዊቷ የትዳር አጋር ብቻ ሳይሆኑ፣ በህይወት ጉዟዋ ሁሉ ከጎኗ የቆሙ ፅኑ ደጋፊዋ፣ የደስታዋ ተካፋይ እና የልብ ወዳጇ ነበሩ።
ገነት ሆይ! የሰው ልጅ ውጫዊ አካሉ ቢያልፍም፣ አብራችሁ ያሳለፋችሁት መልካም ጊዜ፣ የተካፈላችሁት ጥልቅ ፍቅር፣ እና ያፈራችኋቸው አራት ውድ ልጆች ሁሌም ከጎንሽ ሆነው የህያውነቱ ማረጋገጫ ይሆናሉና በርቺ... ፅኚ! ሀዘንሽን እንጋራለን፤ ፈጣሪ ልብሽን ያፅናው።
የዚህ የተከበሩ የቤተሰብ አባት እና ውድ የትዳር አጋር የቀብር ስነስርዓት፣ ሐምሌ 29 ቀን 2018 ዓ.ም በቦሌ አራብሳ ደብረ ገነት ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን ከቀኑ 6፡00 ሰዓት ላይ ወዳጅ ዘመዶቻቸው፣ የጥበብ ቤተሰቦች እና አድናቂዎቻቸው በተገኙበት የሚፈፀም ይሆናል።
ነፍሳቸውን ፈጣሪ በገነት ያኑርልን!
አቶ አዱኛ ይስማቸው የልጅነት አየራቸውን በተነፈሱባት እና በተወለዱባት ታሪካዊቷ የጎንደር ምድር፣ ልዩ ስሟ እንፍራዝ በተባለችው ውብ ከተማ በ1948 ዓ.ም ነበር ወደዚህ ዓለም የመጡት። በምድራዊ የህይወት ጉዟቸውም በውጣ ውረድ ውስጥ አልፈው 70 የተከበሩ ዓመታትን አስቆጥረዋል።
ድምፃዊት ገነት እና አቶ አዱኛ በፍቅር እና በመከባበር የታነፀ ፅኑ ትዳርን መስርተው፣ የትዳራቸው የፍቅር ማሳያ የሆኑ ሁለት ወንድ እና ሁለት ሴት ልጆችን አፍርተዋል። አቶ አዱኛ ለድምፃዊቷ የትዳር አጋር ብቻ ሳይሆኑ፣ በህይወት ጉዟዋ ሁሉ ከጎኗ የቆሙ ፅኑ ደጋፊዋ፣ የደስታዋ ተካፋይ እና የልብ ወዳጇ ነበሩ።
ገነት ሆይ! የሰው ልጅ ውጫዊ አካሉ ቢያልፍም፣ አብራችሁ ያሳለፋችሁት መልካም ጊዜ፣ የተካፈላችሁት ጥልቅ ፍቅር፣ እና ያፈራችኋቸው አራት ውድ ልጆች ሁሌም ከጎንሽ ሆነው የህያውነቱ ማረጋገጫ ይሆናሉና በርቺ... ፅኚ! ሀዘንሽን እንጋራለን፤ ፈጣሪ ልብሽን ያፅናው።
የዚህ የተከበሩ የቤተሰብ አባት እና ውድ የትዳር አጋር የቀብር ስነስርዓት፣ ሐምሌ 29 ቀን 2018 ዓ.ም በቦሌ አራብሳ ደብረ ገነት ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን ከቀኑ 6፡00 ሰዓት ላይ ወዳጅ ዘመዶቻቸው፣ የጥበብ ቤተሰቦች እና አድናቂዎቻቸው በተገኙበት የሚፈፀም ይሆናል።
ነፍሳቸውን ፈጣሪ በገነት ያኑርልን!
2 days ago
በትግራይ «70 ካሬ» የተፈናቃዮች ማዕከል በጣለው ከባድ ዝናብ እና ንፋስ ከ20 በላይ ጊዜያዊ መጠለያዎች ሙሉ በሙሉ ወደሙ፡፡
የምዕራብ ትግራይ ሲቪል ማህበረሰብ ድርጅት (ፅላል) አስተባባሪ አቶ ዘበኖም ኪዱ ለትግራይ ቲቪ እንደገለጹት፤ ትላንት በጣለው ከባድ ዝናብ እና ንፋስ መጠለያዎቹ ከጥቅም ውጪ ከመሆናቸውም በላይ በንብረት ላይ ከፍተኛ ኪሳራ ደርሷል።
በተጨማሪም አደጋው በሰዎች ላይ አካላዊ ጉዳት ያደረሰ ሲሆን፣ በተለይም አረጋውያን ላይ ጉዳት በመድረሱ ለሕክምና እርዳታ ወደ ጤና ተቋም መወሰዳቸውን አስተባባሪው ጨምረው ገልጸዋል።
በደረሰው አደጋ ምክንያት ተፈናቃዮቹ ለበለጠ እንግልት እና ችግር መጋለጣቸውን የጠቆሙት አቶ ዘበኖም፣ የሰብአዊነት ስሜት ያለው አካል ሁሉ አስቸኳይ ድጋፍ እንዲያደርግ ጥሪ አቅርበዋል።
የተፈናቀለው ሕዝብ በከባድ ችግር ውስጥ እንደሚገኝ ያመለከተው የምዕራብ ትግራይ ሲቪል ማህበረሰብ ድርጅት፣ ለችግሩ ዘላቂ መፍትሔ የሚሆነው ተፈናቃዮች ወደ ቀደመ መኖሪያቸው የሚመለሱበት ሁኔታ ሲመቻች ብቻ እንደሆነ አጽንኦት ሰጥቷል ሲል ዘገባው መልክቷል።
Seledadotio
Seledadotio
የምዕራብ ትግራይ ሲቪል ማህበረሰብ ድርጅት (ፅላል) አስተባባሪ አቶ ዘበኖም ኪዱ ለትግራይ ቲቪ እንደገለጹት፤ ትላንት በጣለው ከባድ ዝናብ እና ንፋስ መጠለያዎቹ ከጥቅም ውጪ ከመሆናቸውም በላይ በንብረት ላይ ከፍተኛ ኪሳራ ደርሷል።
በተጨማሪም አደጋው በሰዎች ላይ አካላዊ ጉዳት ያደረሰ ሲሆን፣ በተለይም አረጋውያን ላይ ጉዳት በመድረሱ ለሕክምና እርዳታ ወደ ጤና ተቋም መወሰዳቸውን አስተባባሪው ጨምረው ገልጸዋል።
በደረሰው አደጋ ምክንያት ተፈናቃዮቹ ለበለጠ እንግልት እና ችግር መጋለጣቸውን የጠቆሙት አቶ ዘበኖም፣ የሰብአዊነት ስሜት ያለው አካል ሁሉ አስቸኳይ ድጋፍ እንዲያደርግ ጥሪ አቅርበዋል።
የተፈናቀለው ሕዝብ በከባድ ችግር ውስጥ እንደሚገኝ ያመለከተው የምዕራብ ትግራይ ሲቪል ማህበረሰብ ድርጅት፣ ለችግሩ ዘላቂ መፍትሔ የሚሆነው ተፈናቃዮች ወደ ቀደመ መኖሪያቸው የሚመለሱበት ሁኔታ ሲመቻች ብቻ እንደሆነ አጽንኦት ሰጥቷል ሲል ዘገባው መልክቷል።
Seledadotio
Seledadotio
2 days ago
ኢትዮጵያ እየተጠናቀቀ ባለው 2018 ዓ.ም ከ124 በላይ ዓለም አቀፍ ሜዳሊያዎች መገኘታቸውን ተገለጸ
#ethiopia | በኢትዮጵያ የስፖርት ዘርፍ አዲስ እይታን በመፍጠር፣ ህጋዊና መዋቅራዊ ማዕቀፎችን በማጠናከር እንዲሁም በርካታ ሀገር አቀፍና ዓለም አቀፍ ውድድሮችን በማስተናገድ የ2018 በጀት ዓመት አመርቂና ስኬታማ ጊዜ የነበረ መሆኑ ተገለጸ።
የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር የሚያካሄደው የባህል፣ ጥበባትና ስፖርት ጥናትና ምርምር ጉባኤ እንዲሁም ዓመታዊ የሴክተር ጉባኤ ላይ የባህል እና ስፖርት ሚኒስቴር የስፖርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ድኤታ አቶ መክዩ መሀመድ እንደገለጹት፣ የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ዓመታዊ የሴክተር ጉባኤ የታቀዱ ግቦችን በጋራ ለመገምገም እና ከክልል እስከ ፌደራል ያሉ ቅንጅታዊ አሰራሮችን ለማጠናከር ከፍተኛ አስተዋጽኦ አበርክቷል።
አክለውም ዘንድሮ የስፖርት ልማት ስራዎች በተሻለ መንገድ የተፈጸሙበትና በአጠቃላይ የስፖርት ዘመን ተብሎ ሊወሰድ የሚችልበት የስኬት ዓመት እንደነበር ጠቁመዋል።
የስፖርት ቤተሰቡ በተደጋጋሚ ያነሳቸው የነበሩ ህጋዊና አሰራር ነክ ጥያቄዎች ምላሽ ማግኘታቸውን የጠቆሙት ሚኒስትር ድኤታው፣ ሁሉንም ባለድርሻ አካላትና ምሁራንን ያሳተፈ አዲስ የስፖርት ፖሊሲ ተዘጋጅቶ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መጽደቁንና አዋጁም ወደ ትግበራ መግባቱን አስረድተዋል።
ይህ አዲስ ፖሊሲ የመንግስትን አመራር ሰጪነት፣ ከ139 ሺህ በላይ የሚሆኑ ህዝባዊ አደረጃጀቶችንና ማህበራትን አቅጣጫ፣ እንዲሁም የስፖርቱን እድገት የሚያፋጥነው የግል ባለሀብቶች ተሳትፎን በግልጽ የለየ አዲስ እይታ ይዞ መምጣቱንም አብራርተዋል።
ስፖርት ከሜዳ ውድድር ባለፈ የህዝቦች ወንድማማችነትን የሚገነባ፣ ሰላምና አንድነትን የሚያጠናክር ትልቅ የሀገር ልማት መሳሪያ መሆኑን የገለጹት አቶ መክዩ መሀመድ፣ በዚህ ዓመት በተካሄዱ 420 የክልል አቀፍ እና 118 ሀገር አቀፍ ውድድሮች ከአስር ሺዎች በላይ ስፖርተኞች መሳተፋቸውን ገልጸዋል። እነዚህ መድረኮች የወጡ አትሌቶችን ከማፍራት ባሻገር ሰላምን በመገንባትና ህዝቦችን በማቀራረብ ረገድ የጎላ ሚና እንደነበራቸው አብራርተዋል።
ህብረተሰቡን ንቁና ስፖርትን ባህል ያደረገ ለማድረግ በተሰራው ስራ የስፖርት አዘዋታሪው ህዝብ ቁጥር 24 በመቶ ወይም 32 ሚሊዮን ማድረስ መቻሉን ሚኒስትር ድኤታው ጠቁመዋል። ከዚህ በተጨማሪ ከኮሪደር ልማት ጋር በተያያዘ ከ45 ሺህ በላይ የስፖርት ፋሲሊቲዎች መገንባታቸውንና እነዚህንም በቴክኖሎጂ ዘመናዊ የማድረግ ስራ እየተከናወነ እንደሚገኝ ገልጸዋል።
በአለም አቀፍና ቀጠናዊ ውድድሮች የሀገሪቱን ስም የሚያስጠሩ አሸናፊ ብሄራዊ ቡድኖችን ለመገንባት በሚደረገው ጥረት አትሌቶቻችን ከ124 በላይ ሜዳሊያዎችን ማስመዝገባቸውን አቶ መክዩ መሀመድ አበክረው ገልጸዋል።
በተለይም በታዳጊዎች ልማት ላይ ትኩረት ተደርጎ እየተሰራ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት ከ45 ሺህ በላይ ታዳጊዎች በማሰልጠኛ ማዕከላት ውስጥ ስልጠና እየወሰዱ ይገኛሉ።
በተጨማሪም የስፖርት ቱሪዝምን ለማበራታት በተደረገው ጥረት ከ29 በላይ ዓለም አቀፍ ውድድሮችና ኮንፈረንሶች በኢትዮጵያ መካሄዳቸውንና ደረጃቸውን የጠበቁ ስታዲየሞች ግንባታም ትኩረት ተሰጥቶት እየተከናወነ መሆኑን ጠቅሰዋል።
ስፖርት ለሀገር ጂዲፒ እና ለስራ እድል ፈጠራ የሚያበረክተውን አስተዋጽኦ ለማሳደግ የተጀመሩ ጥናቶች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ አብራርተዋል።
በመጨረሻም፣ በአዲሱ ፖሊሲ የባህል ስፖርት ልዩ ትኩረት ማግኘቱንና በቀጣይ ዓመት ኢትዮጵያ የአፍሪካ የባህል ስፖርት ፌስቲቫልን በበላይነት እንደምታዘጋጅ አቶ መክዩ መሀመድ ገልጸው፤ ላመጣው ስኬት ለስፖርት ቤተሰቡና ለመገናኛ ብዙሃን አካላት ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
ጌትነት ተመስገን
📷 ከበደ መክብብ
#ethiopiansports #ethiopiasportpolicy #sportsdevelopment #ethiopia#youthinsports #sportinspiration
#ethiopia | በኢትዮጵያ የስፖርት ዘርፍ አዲስ እይታን በመፍጠር፣ ህጋዊና መዋቅራዊ ማዕቀፎችን በማጠናከር እንዲሁም በርካታ ሀገር አቀፍና ዓለም አቀፍ ውድድሮችን በማስተናገድ የ2018 በጀት ዓመት አመርቂና ስኬታማ ጊዜ የነበረ መሆኑ ተገለጸ።
የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር የሚያካሄደው የባህል፣ ጥበባትና ስፖርት ጥናትና ምርምር ጉባኤ እንዲሁም ዓመታዊ የሴክተር ጉባኤ ላይ የባህል እና ስፖርት ሚኒስቴር የስፖርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ድኤታ አቶ መክዩ መሀመድ እንደገለጹት፣ የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ዓመታዊ የሴክተር ጉባኤ የታቀዱ ግቦችን በጋራ ለመገምገም እና ከክልል እስከ ፌደራል ያሉ ቅንጅታዊ አሰራሮችን ለማጠናከር ከፍተኛ አስተዋጽኦ አበርክቷል።
አክለውም ዘንድሮ የስፖርት ልማት ስራዎች በተሻለ መንገድ የተፈጸሙበትና በአጠቃላይ የስፖርት ዘመን ተብሎ ሊወሰድ የሚችልበት የስኬት ዓመት እንደነበር ጠቁመዋል።
የስፖርት ቤተሰቡ በተደጋጋሚ ያነሳቸው የነበሩ ህጋዊና አሰራር ነክ ጥያቄዎች ምላሽ ማግኘታቸውን የጠቆሙት ሚኒስትር ድኤታው፣ ሁሉንም ባለድርሻ አካላትና ምሁራንን ያሳተፈ አዲስ የስፖርት ፖሊሲ ተዘጋጅቶ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መጽደቁንና አዋጁም ወደ ትግበራ መግባቱን አስረድተዋል።
ይህ አዲስ ፖሊሲ የመንግስትን አመራር ሰጪነት፣ ከ139 ሺህ በላይ የሚሆኑ ህዝባዊ አደረጃጀቶችንና ማህበራትን አቅጣጫ፣ እንዲሁም የስፖርቱን እድገት የሚያፋጥነው የግል ባለሀብቶች ተሳትፎን በግልጽ የለየ አዲስ እይታ ይዞ መምጣቱንም አብራርተዋል።
ስፖርት ከሜዳ ውድድር ባለፈ የህዝቦች ወንድማማችነትን የሚገነባ፣ ሰላምና አንድነትን የሚያጠናክር ትልቅ የሀገር ልማት መሳሪያ መሆኑን የገለጹት አቶ መክዩ መሀመድ፣ በዚህ ዓመት በተካሄዱ 420 የክልል አቀፍ እና 118 ሀገር አቀፍ ውድድሮች ከአስር ሺዎች በላይ ስፖርተኞች መሳተፋቸውን ገልጸዋል። እነዚህ መድረኮች የወጡ አትሌቶችን ከማፍራት ባሻገር ሰላምን በመገንባትና ህዝቦችን በማቀራረብ ረገድ የጎላ ሚና እንደነበራቸው አብራርተዋል።
ህብረተሰቡን ንቁና ስፖርትን ባህል ያደረገ ለማድረግ በተሰራው ስራ የስፖርት አዘዋታሪው ህዝብ ቁጥር 24 በመቶ ወይም 32 ሚሊዮን ማድረስ መቻሉን ሚኒስትር ድኤታው ጠቁመዋል። ከዚህ በተጨማሪ ከኮሪደር ልማት ጋር በተያያዘ ከ45 ሺህ በላይ የስፖርት ፋሲሊቲዎች መገንባታቸውንና እነዚህንም በቴክኖሎጂ ዘመናዊ የማድረግ ስራ እየተከናወነ እንደሚገኝ ገልጸዋል።
በአለም አቀፍና ቀጠናዊ ውድድሮች የሀገሪቱን ስም የሚያስጠሩ አሸናፊ ብሄራዊ ቡድኖችን ለመገንባት በሚደረገው ጥረት አትሌቶቻችን ከ124 በላይ ሜዳሊያዎችን ማስመዝገባቸውን አቶ መክዩ መሀመድ አበክረው ገልጸዋል።
በተለይም በታዳጊዎች ልማት ላይ ትኩረት ተደርጎ እየተሰራ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት ከ45 ሺህ በላይ ታዳጊዎች በማሰልጠኛ ማዕከላት ውስጥ ስልጠና እየወሰዱ ይገኛሉ።
በተጨማሪም የስፖርት ቱሪዝምን ለማበራታት በተደረገው ጥረት ከ29 በላይ ዓለም አቀፍ ውድድሮችና ኮንፈረንሶች በኢትዮጵያ መካሄዳቸውንና ደረጃቸውን የጠበቁ ስታዲየሞች ግንባታም ትኩረት ተሰጥቶት እየተከናወነ መሆኑን ጠቅሰዋል።
ስፖርት ለሀገር ጂዲፒ እና ለስራ እድል ፈጠራ የሚያበረክተውን አስተዋጽኦ ለማሳደግ የተጀመሩ ጥናቶች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ አብራርተዋል።
በመጨረሻም፣ በአዲሱ ፖሊሲ የባህል ስፖርት ልዩ ትኩረት ማግኘቱንና በቀጣይ ዓመት ኢትዮጵያ የአፍሪካ የባህል ስፖርት ፌስቲቫልን በበላይነት እንደምታዘጋጅ አቶ መክዩ መሀመድ ገልጸው፤ ላመጣው ስኬት ለስፖርት ቤተሰቡና ለመገናኛ ብዙሃን አካላት ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
ጌትነት ተመስገን
📷 ከበደ መክብብ
#ethiopiansports #ethiopiasportpolicy #sportsdevelopment #ethiopia#youthinsports #sportinspiration
2 days ago
ኢትዮ-ኢስታንቡል ሆስፒታል በዓመት ከ79 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች ህክምና መስጠቱን ገለጸ
#ethiopia | ኢትዮ-ኢስታንቡል ጠቅላላ ሆስፒታል በተመሰረተ በአጭር ጊዜ ወደውጭ ሀገር በሚወስዱ የህክምና ጥገኝነትን በመቀየር፣ በሀገር ውስጥ ዘመናዊ ህክምና መስጠት የሚያስችል አገልግሎት መዘርጋቱን አስታወቀ።
ኢትዮ-ኢስታንቡል አጠቃላይ ሆስፒታል ሐምሌ 28 ቀን 2018 ዓ.ም ለመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች በሰጠው መግለጫ ላይ እንደተገለጸው ሆስፒታሉ በመሥራቹና ባለራዕዩ ሲኢኦ አቶ ብርሃን ተድላ እየተመራ ከተመሰረተበት ጊዜ ጀምሮ ለታካሚዎች ጥራቱን የጠበቀ የሕክምና አገልግሎት ሲሰጥ የቆየ ሲሆን፣ በተለይም በያዝነው 2018 ዓ.ም ብቻ ከ79 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የተመላላሽ ህክምና አገልግሎት በመስጠትና ከ4 ሺ 500 በላይ የቀዶ ህክምናዎችን በማካሄድ አመርቂ ውጤት አስመዝግቧል።
ሆስፒታሉ እነዚህን ሀገር በቀል አቅሞች በመገንባቱ ቀደም ሲል ለህክምና ወደ ውጭ ሀገር ይሄዱ የነበሩ ታካሚዎችን ቁጥር በመቀነስ የውጭ ምንዛሬን ከማስቀረት ባሻገር የታካሚዎችን ችግር መቅረፍ ችሏል።
በመግለጫው ወቅት የሆስፒታሉ ሜዲካል ዳይሬክተር፣ የአጠቃላይ እና ደረት አካባቢ ቀዶ ህክምና ስፔሻሊስት ተባባሪ ኘሮፌሰር ስዩም ካሣ መርኔ እንደገለጹት፣ ተቋሙ በኢንተርቬንሽናል ካርዲዮሎጂ መስክ ያለ ኦፕሬሽን በደም ስሮች በኩል በሚደረግ ህክምና ጨምሮ በአዋቂና በልጆች የልብ ሕክምና በአጠቃላይ ከ735 በላይ ታካሚዎችን መታደግ ችሏል። አክለውም ይህ አገልግሎት ዓመቱን ሙሉ ሌሊትና ቀን ሳይቋረጥ የሚሰጥ በመሆኑ፣ ከውጭ ሀገር በሚመጡ ጊዜያዊ ዘመቻዎች ላይ ብቻ ጥገኛ የነበረውን አሰራር መቀየር መቻሉን ገልጸዋል።
ሆስፒታሉ በኢትዮጵያውያን ባለሙያዎች በመታገዝ ወደውጪ ሀገር የሚያስኬዱ በተለይ የልብ ሕክምናዎችን 90 በመቶ በሆስፒታሉ መስጠት መቻሉን ጠቅሰዋል።
እንደ ዶክተር ስዩም ገለጻ፣ ሆስፒታሉ በኒውሮሰርጀሪ፣ በኦፕን ካርዲያክ፣ በአጥንትና ስፓይን፣ በኩላሊት፣ በሳምባ፣ የአንጎል፣ የዳሌና የጉልበት ቅየራ እንዲሁም በሚኒማሊ ኢንቬሲቭ (ላፓሮስኮፒክና ቶራኮስኮፒክ) እና ከ46 በላይ ሰብስፔሻሊቲ ህክምና ዘርፎች የላቀ አገልግሎት እየሰጠ ሲሆን፣ የሬዲዮሎጂ ክፍሉም የሰው ሰራሽ አስተውሎት ቴክኖሎጂን በመጠቀም የህክምና ምርመራ ጥራቱን በማሳደግ ላይ ይገኛል ብለዋል።
የሆስፒታሉ የውስጥ ደዌና የአዋቂዎች ኢንተርቬንሽናል የልብ ህክምና ስፔሻሊስት ዶክተር ከፈለኝ ደጀኔ በበኩላቸው እንደገለጹት፣ ከተሰሩት 321 የሕፃናት የልብ ህክምናዎች መከናወናቸውን ጠቁመው 90 የሚጠጋ ድንገተኛ የልብ ደምስር መዘጋት አደጋ ያጋጠማቸውና ታካሚዎች በ24 ሰዓት ድንገተኛ አደጋዎች አገልግሎት ህይወታቸው መታደግ ተችላል ብለዋል። ከእነዚህም ውስጥ ቁጥራቸው ከ90 በላይ የሚኾኑ የውጭ ሀገር ዜጎችና ዲፕሎማቶች እንዲሁም ነፍሰጡር እናቶች ይገኙበታል።
የሆስፒታሉ የቺፍ ኦፕሬሽንስ ዳይሬክተር፣ የአንገትና ጭንቅላት ሰብ-ስፔሻሊስት ዶክተር መለስ ገበየሁ እንደገለጹት ደግሞ፣ ተቋሙ ከንግድ ዓላማው ጎን ለጎን ማህበራዊ ኃላፊነቱን በመወጣት ረገድ ትልቅ ስራ እየሰራ ይገኛል። በሆስፒታሉ ባለቤትና ዋና ስራአስፈጻሚ አቶ ብርሃን ተድላ አማካይነት በተቋቋመው "Heart to Heart Children's Aid" የተሰኘ ፋውንዴሽን በኩል ትልቅ ሥራዎች መከናወናቸውን አስታውሰዋል።
ሜዲካል ዳይሬክተሩ በመጨረሻም ኢትዮ ኢስታንቡል ጠቅላላ ሆስፒታል በሰኔ ወር 2015 ዓ.ም ጀምሮ ወደሥራ መግባቱና በአጭር ጊዜ ውስጥ ከፍተኛ ውጤት መድረስ የቻለው በተቋሙ መስራችና ሲኢኦ አቶ ብርሃን ተድላ የቅርብ ጠንካራ አመራርና ክትትል፣ በሰራተኞችና ባለሙያዎች ትጋት መኾኑን በመጥቀስ ምስጋና አቅርበዋል።
ሆስፒታሉ ለ 333 ጊዜያዊና ቋሚ ሰራተኞች የሥራ ዕድል የፈጠረ ሲኾን ከእነዚህ መካከል 86 ያህሉ ሰብስፔሻስት ሐኪሞች መኾናቸው ተነግሯል።
#ethioistanbulhospital #cardiologyservices
#pediatriccardiolog #healthsectorethiopia
#medicaltourismethiopia#hearttoheartchildrensaid
#ethiopia | ኢትዮ-ኢስታንቡል ጠቅላላ ሆስፒታል በተመሰረተ በአጭር ጊዜ ወደውጭ ሀገር በሚወስዱ የህክምና ጥገኝነትን በመቀየር፣ በሀገር ውስጥ ዘመናዊ ህክምና መስጠት የሚያስችል አገልግሎት መዘርጋቱን አስታወቀ።
ኢትዮ-ኢስታንቡል አጠቃላይ ሆስፒታል ሐምሌ 28 ቀን 2018 ዓ.ም ለመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች በሰጠው መግለጫ ላይ እንደተገለጸው ሆስፒታሉ በመሥራቹና ባለራዕዩ ሲኢኦ አቶ ብርሃን ተድላ እየተመራ ከተመሰረተበት ጊዜ ጀምሮ ለታካሚዎች ጥራቱን የጠበቀ የሕክምና አገልግሎት ሲሰጥ የቆየ ሲሆን፣ በተለይም በያዝነው 2018 ዓ.ም ብቻ ከ79 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የተመላላሽ ህክምና አገልግሎት በመስጠትና ከ4 ሺ 500 በላይ የቀዶ ህክምናዎችን በማካሄድ አመርቂ ውጤት አስመዝግቧል።
ሆስፒታሉ እነዚህን ሀገር በቀል አቅሞች በመገንባቱ ቀደም ሲል ለህክምና ወደ ውጭ ሀገር ይሄዱ የነበሩ ታካሚዎችን ቁጥር በመቀነስ የውጭ ምንዛሬን ከማስቀረት ባሻገር የታካሚዎችን ችግር መቅረፍ ችሏል።
በመግለጫው ወቅት የሆስፒታሉ ሜዲካል ዳይሬክተር፣ የአጠቃላይ እና ደረት አካባቢ ቀዶ ህክምና ስፔሻሊስት ተባባሪ ኘሮፌሰር ስዩም ካሣ መርኔ እንደገለጹት፣ ተቋሙ በኢንተርቬንሽናል ካርዲዮሎጂ መስክ ያለ ኦፕሬሽን በደም ስሮች በኩል በሚደረግ ህክምና ጨምሮ በአዋቂና በልጆች የልብ ሕክምና በአጠቃላይ ከ735 በላይ ታካሚዎችን መታደግ ችሏል። አክለውም ይህ አገልግሎት ዓመቱን ሙሉ ሌሊትና ቀን ሳይቋረጥ የሚሰጥ በመሆኑ፣ ከውጭ ሀገር በሚመጡ ጊዜያዊ ዘመቻዎች ላይ ብቻ ጥገኛ የነበረውን አሰራር መቀየር መቻሉን ገልጸዋል።
ሆስፒታሉ በኢትዮጵያውያን ባለሙያዎች በመታገዝ ወደውጪ ሀገር የሚያስኬዱ በተለይ የልብ ሕክምናዎችን 90 በመቶ በሆስፒታሉ መስጠት መቻሉን ጠቅሰዋል።
እንደ ዶክተር ስዩም ገለጻ፣ ሆስፒታሉ በኒውሮሰርጀሪ፣ በኦፕን ካርዲያክ፣ በአጥንትና ስፓይን፣ በኩላሊት፣ በሳምባ፣ የአንጎል፣ የዳሌና የጉልበት ቅየራ እንዲሁም በሚኒማሊ ኢንቬሲቭ (ላፓሮስኮፒክና ቶራኮስኮፒክ) እና ከ46 በላይ ሰብስፔሻሊቲ ህክምና ዘርፎች የላቀ አገልግሎት እየሰጠ ሲሆን፣ የሬዲዮሎጂ ክፍሉም የሰው ሰራሽ አስተውሎት ቴክኖሎጂን በመጠቀም የህክምና ምርመራ ጥራቱን በማሳደግ ላይ ይገኛል ብለዋል።
የሆስፒታሉ የውስጥ ደዌና የአዋቂዎች ኢንተርቬንሽናል የልብ ህክምና ስፔሻሊስት ዶክተር ከፈለኝ ደጀኔ በበኩላቸው እንደገለጹት፣ ከተሰሩት 321 የሕፃናት የልብ ህክምናዎች መከናወናቸውን ጠቁመው 90 የሚጠጋ ድንገተኛ የልብ ደምስር መዘጋት አደጋ ያጋጠማቸውና ታካሚዎች በ24 ሰዓት ድንገተኛ አደጋዎች አገልግሎት ህይወታቸው መታደግ ተችላል ብለዋል። ከእነዚህም ውስጥ ቁጥራቸው ከ90 በላይ የሚኾኑ የውጭ ሀገር ዜጎችና ዲፕሎማቶች እንዲሁም ነፍሰጡር እናቶች ይገኙበታል።
የሆስፒታሉ የቺፍ ኦፕሬሽንስ ዳይሬክተር፣ የአንገትና ጭንቅላት ሰብ-ስፔሻሊስት ዶክተር መለስ ገበየሁ እንደገለጹት ደግሞ፣ ተቋሙ ከንግድ ዓላማው ጎን ለጎን ማህበራዊ ኃላፊነቱን በመወጣት ረገድ ትልቅ ስራ እየሰራ ይገኛል። በሆስፒታሉ ባለቤትና ዋና ስራአስፈጻሚ አቶ ብርሃን ተድላ አማካይነት በተቋቋመው "Heart to Heart Children's Aid" የተሰኘ ፋውንዴሽን በኩል ትልቅ ሥራዎች መከናወናቸውን አስታውሰዋል።
ሜዲካል ዳይሬክተሩ በመጨረሻም ኢትዮ ኢስታንቡል ጠቅላላ ሆስፒታል በሰኔ ወር 2015 ዓ.ም ጀምሮ ወደሥራ መግባቱና በአጭር ጊዜ ውስጥ ከፍተኛ ውጤት መድረስ የቻለው በተቋሙ መስራችና ሲኢኦ አቶ ብርሃን ተድላ የቅርብ ጠንካራ አመራርና ክትትል፣ በሰራተኞችና ባለሙያዎች ትጋት መኾኑን በመጥቀስ ምስጋና አቅርበዋል።
ሆስፒታሉ ለ 333 ጊዜያዊና ቋሚ ሰራተኞች የሥራ ዕድል የፈጠረ ሲኾን ከእነዚህ መካከል 86 ያህሉ ሰብስፔሻስት ሐኪሞች መኾናቸው ተነግሯል።
#ethioistanbulhospital #cardiologyservices
#pediatriccardiolog #healthsectorethiopia
#medicaltourismethiopia#hearttoheartchildrensaid
2 days ago
ኢትዮ-ኢስታንቡል ሆስፒታል በዓመት ከ79 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች ህክምና መስጠቱን ገለጸ
ኢትዮ-ኢስታንቡል ጠቅላላ ሆስፒታል በተመሰረተ በአጭር ጊዜ ወደውጭ ሀገር በሚወስዱ የህክምና ጥገኝነትን በመቀየር፣ በሀገር ውስጥ ዘመናዊ ህክምና መስጠት የሚያስችል አገልግሎት መዘርጋቱን አስታወቀ።
ኢትዮ-ኢስታንቡል አጠቃላይ ሆስፒታል ሐምሌ 28 ቀን 2018 ዓ.ም ለመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች በሰጠው መግለጫ ላይ እንደተገለጸው ሆስፒታሉ በመሥራቹና ባለራዕዩ ሲኢኦ አቶ ብርሃን ተድላ እየተመራ ከተመሰረተበት ጊዜ ጀምሮ ለታካሚዎች ጥራቱን የጠበቀ የሕክምና አገልግሎት ሲሰጥ የቆየ ሲሆን፣ በተለይም በያዝነው 2018 ዓ.ም ብቻ ከ79 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የተመላላሽ ህክምና አገልግሎት በመስጠትና ከ4 ሺ 500 በላይ የቀዶ ህክምናዎችን በማካሄድ አመርቂ ውጤት አስመዝግቧል።
ሆስፒታሉ እነዚህን ሀገር በቀል አቅሞች በመገንባቱ ቀደም ሲል ለህክምና ወደ ውጭ ሀገር ይሄዱ የነበሩ ታካሚዎችን ቁጥር በመቀነስ የውጭ ምንዛሬን ከማስቀረት ባሻገር የታካሚዎችን ችግር መቅረፍ ችሏል።
በመግለጫው ወቅት የሆስፒታሉ ሜዲካል ዳይሬክተር፣ የአጠቃላይ እና ደረት አካባቢ ቀዶ ህክምና ስፔሻሊስት ተባባሪ ኘሮፌሰር ስዩም ካሣ መርኔ እንደገለጹት፣ ተቋሙ በኢንተርቬንሽናል ካርዲዮሎጂ መስክ ያለ ኦፕሬሽን በደም ስሮች በኩል በሚደረግ ህክምና ጨምሮ በአዋቂና በልጆች የልብ ሕክምና በአጠቃላይ ከ735 በላይ ታካሚዎችን መታደግ ችሏል። አክለውም ይህ አገልግሎት ዓመቱን ሙሉ ሌሊትና ቀን ሳይቋረጥ የሚሰጥ በመሆኑ፣ ከውጭ ሀገር በሚመጡ ጊዜያዊ ዘመቻዎች ላይ ብቻ ጥገኛ የነበረውን አሰራር መቀየር መቻሉን ገልጸዋል።
ሆስፒታሉ በኢትዮጵያውያን ባለሙያዎች በመታገዝ ወደውጪ ሀገር የሚያስኬዱ በተለይ የልብ ሕክምናዎችን 90 በመቶ በሆስፒታሉ መስጠት መቻሉን ጠቅሰዋል።
እንደ ዶክተር ስዩም ገለጻ፣ ሆስፒታሉ በኒውሮሰርጀሪ፣ በኦፕን ካርዲያክ፣ በአጥንትና ስፓይን፣ በኩላሊት፣ በሳምባ፣ የአንጎል፣ የዳሌና የጉልበት ቅየራ እንዲሁም በሚኒማሊ ኢንቬሲቭ (ላፓሮስኮፒክና ቶራኮስኮፒክ) እና ከ46 በላይ ሰብስፔሻሊቲ ህክምና ዘርፎች የላቀ አገልግሎት እየሰጠ ሲሆን፣ የሬዲዮሎጂ ክፍሉም የሰው ሰራሽ አስተውሎት ቴክኖሎጂን በመጠቀም የህክምና ምርመራ ጥራቱን በማሳደግ ላይ ይገኛል ብለዋል።
የሆስፒታሉ የውስጥ ደዌና የአዋቂዎች ኢንተርቬንሽናል የልብ ህክምና ስፔሻሊስት ዶክተር ከፈለኝ ደጀኔ በበኩላቸው እንደገለጹት፣ ከተሰሩት 321 የሕፃናት የልብ ህክምናዎች መከናወናቸውን ጠቁመው 90 የሚጠጋ ድንገተኛ የልብ ደምስር መዘጋት አደጋ ያጋጠማቸውና ታካሚዎች በ24 ሰዓት ድንገተኛ አደጋዎች አገልግሎት ህይወታቸው መታደግ ተችላል ብለዋል። ከእነዚህም ውስጥ ቁጥራቸው ከ90 በላይ የሚኾኑ የውጭ ሀገር ዜጎችና ዲፕሎማቶች እንዲሁም ነፍሰጡር እናቶች ይገኙበታል።
የሆስፒታሉ የቺፍ ኦፕሬሽንስ ዳይሬክተር፣ የአንገትና ጭንቅላት ሰብ-ስፔሻሊስት ዶክተር መለስ ገበየሁ እንደገለጹት ደግሞ፣ ተቋሙ ከንግድ ዓላማው ጎን ለጎን ማህበራዊ ኃላፊነቱን በመወጣት ረገድ ትልቅ ስራ እየሰራ ይገኛል። በሆስፒታሉ ባለቤትና ዋና ስራአስፈጻሚ አቶ ብርሃን ተድላ አማካይነት በተቋቋመው "Heart to Heart Children's Aid" የተሰኘ ፋውንዴሽን በኩል ትልቅ ሥራዎች መከናወናቸውን አስታውሰዋል።
ሜዲካል ዳይሬክተሩ በመጨረሻም ኢትዮ ኢስታንቡል ጠቅላላ ሆስፒታል በሰኔ ወር 2015 ዓ.ም ጀምሮ ወደሥራ መግባቱና በአጭር ጊዜ ውስጥ ከፍተኛ ውጤት መድረስ የቻለው በተቋሙ መስራችና ሲኢኦ አቶ ብርሃን ተድላ የቅርብ ጠንካራ አመራርና ክትትል፣ በሰራተኞችና ባለሙያዎች ትጋት መኾኑን በመጥቀስ ምስጋና አቅርበዋል።
ሆስፒታሉ ለ 333 ጊዜያዊና ቋሚ ሰራተኞች የሥራ ዕድል የፈጠረ ሲኾን ከእነዚህ መካከል 86 ያህሉ ሰብስፔሻስት ሐኪሞች መኾናቸው ተነግሯል።
ኢትዮ-ኢስታንቡል ጠቅላላ ሆስፒታል በተመሰረተ በአጭር ጊዜ ወደውጭ ሀገር በሚወስዱ የህክምና ጥገኝነትን በመቀየር፣ በሀገር ውስጥ ዘመናዊ ህክምና መስጠት የሚያስችል አገልግሎት መዘርጋቱን አስታወቀ።
ኢትዮ-ኢስታንቡል አጠቃላይ ሆስፒታል ሐምሌ 28 ቀን 2018 ዓ.ም ለመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች በሰጠው መግለጫ ላይ እንደተገለጸው ሆስፒታሉ በመሥራቹና ባለራዕዩ ሲኢኦ አቶ ብርሃን ተድላ እየተመራ ከተመሰረተበት ጊዜ ጀምሮ ለታካሚዎች ጥራቱን የጠበቀ የሕክምና አገልግሎት ሲሰጥ የቆየ ሲሆን፣ በተለይም በያዝነው 2018 ዓ.ም ብቻ ከ79 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የተመላላሽ ህክምና አገልግሎት በመስጠትና ከ4 ሺ 500 በላይ የቀዶ ህክምናዎችን በማካሄድ አመርቂ ውጤት አስመዝግቧል።
ሆስፒታሉ እነዚህን ሀገር በቀል አቅሞች በመገንባቱ ቀደም ሲል ለህክምና ወደ ውጭ ሀገር ይሄዱ የነበሩ ታካሚዎችን ቁጥር በመቀነስ የውጭ ምንዛሬን ከማስቀረት ባሻገር የታካሚዎችን ችግር መቅረፍ ችሏል።
በመግለጫው ወቅት የሆስፒታሉ ሜዲካል ዳይሬክተር፣ የአጠቃላይ እና ደረት አካባቢ ቀዶ ህክምና ስፔሻሊስት ተባባሪ ኘሮፌሰር ስዩም ካሣ መርኔ እንደገለጹት፣ ተቋሙ በኢንተርቬንሽናል ካርዲዮሎጂ መስክ ያለ ኦፕሬሽን በደም ስሮች በኩል በሚደረግ ህክምና ጨምሮ በአዋቂና በልጆች የልብ ሕክምና በአጠቃላይ ከ735 በላይ ታካሚዎችን መታደግ ችሏል። አክለውም ይህ አገልግሎት ዓመቱን ሙሉ ሌሊትና ቀን ሳይቋረጥ የሚሰጥ በመሆኑ፣ ከውጭ ሀገር በሚመጡ ጊዜያዊ ዘመቻዎች ላይ ብቻ ጥገኛ የነበረውን አሰራር መቀየር መቻሉን ገልጸዋል።
ሆስፒታሉ በኢትዮጵያውያን ባለሙያዎች በመታገዝ ወደውጪ ሀገር የሚያስኬዱ በተለይ የልብ ሕክምናዎችን 90 በመቶ በሆስፒታሉ መስጠት መቻሉን ጠቅሰዋል።
እንደ ዶክተር ስዩም ገለጻ፣ ሆስፒታሉ በኒውሮሰርጀሪ፣ በኦፕን ካርዲያክ፣ በአጥንትና ስፓይን፣ በኩላሊት፣ በሳምባ፣ የአንጎል፣ የዳሌና የጉልበት ቅየራ እንዲሁም በሚኒማሊ ኢንቬሲቭ (ላፓሮስኮፒክና ቶራኮስኮፒክ) እና ከ46 በላይ ሰብስፔሻሊቲ ህክምና ዘርፎች የላቀ አገልግሎት እየሰጠ ሲሆን፣ የሬዲዮሎጂ ክፍሉም የሰው ሰራሽ አስተውሎት ቴክኖሎጂን በመጠቀም የህክምና ምርመራ ጥራቱን በማሳደግ ላይ ይገኛል ብለዋል።
የሆስፒታሉ የውስጥ ደዌና የአዋቂዎች ኢንተርቬንሽናል የልብ ህክምና ስፔሻሊስት ዶክተር ከፈለኝ ደጀኔ በበኩላቸው እንደገለጹት፣ ከተሰሩት 321 የሕፃናት የልብ ህክምናዎች መከናወናቸውን ጠቁመው 90 የሚጠጋ ድንገተኛ የልብ ደምስር መዘጋት አደጋ ያጋጠማቸውና ታካሚዎች በ24 ሰዓት ድንገተኛ አደጋዎች አገልግሎት ህይወታቸው መታደግ ተችላል ብለዋል። ከእነዚህም ውስጥ ቁጥራቸው ከ90 በላይ የሚኾኑ የውጭ ሀገር ዜጎችና ዲፕሎማቶች እንዲሁም ነፍሰጡር እናቶች ይገኙበታል።
የሆስፒታሉ የቺፍ ኦፕሬሽንስ ዳይሬክተር፣ የአንገትና ጭንቅላት ሰብ-ስፔሻሊስት ዶክተር መለስ ገበየሁ እንደገለጹት ደግሞ፣ ተቋሙ ከንግድ ዓላማው ጎን ለጎን ማህበራዊ ኃላፊነቱን በመወጣት ረገድ ትልቅ ስራ እየሰራ ይገኛል። በሆስፒታሉ ባለቤትና ዋና ስራአስፈጻሚ አቶ ብርሃን ተድላ አማካይነት በተቋቋመው "Heart to Heart Children's Aid" የተሰኘ ፋውንዴሽን በኩል ትልቅ ሥራዎች መከናወናቸውን አስታውሰዋል።
ሜዲካል ዳይሬክተሩ በመጨረሻም ኢትዮ ኢስታንቡል ጠቅላላ ሆስፒታል በሰኔ ወር 2015 ዓ.ም ጀምሮ ወደሥራ መግባቱና በአጭር ጊዜ ውስጥ ከፍተኛ ውጤት መድረስ የቻለው በተቋሙ መስራችና ሲኢኦ አቶ ብርሃን ተድላ የቅርብ ጠንካራ አመራርና ክትትል፣ በሰራተኞችና ባለሙያዎች ትጋት መኾኑን በመጥቀስ ምስጋና አቅርበዋል።
ሆስፒታሉ ለ 333 ጊዜያዊና ቋሚ ሰራተኞች የሥራ ዕድል የፈጠረ ሲኾን ከእነዚህ መካከል 86 ያህሉ ሰብስፔሻስት ሐኪሞች መኾናቸው ተነግሯል።
2 days ago
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ረጅም ርቀት መጓዝ የሚችሉ አውሮፕላኖች ግዢ እየተከናወነ ነው
አየር መንገዱ ወደ አውስትራሊያ በረራ የመጀመር ከፍተኛ ፍላጎት እንዳለውና ገበያውም እንዳለ መረዳቱን የአየር መንገዱ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ጣሰው ተናግረዋል።
ነገር ግን አሁን ላይ ወደ አውስትራልያ በረራ ለመጀመር " አውሮፕላን የለንም " ብለዋል።
ለዚህም ረጅም ርቀት መጓዝ የሚችሉ አዳዲስ አውሮፕላኖች ግዢ እየተከናወነ መሆኑን ተጠቁሟል።
አየር መንገዱ ከጥር 2020 ዓ.ም ጀምሮ ከቦይንግ እና ኤርባስ ኩባንያዎች የሚረከባቸው በርከት ያሉ አዳዲስ አውሮፕላኖች በመኖራቸው ለአውስትራሊያው መስመር በረራ መጀመር ዝግጅት እንደሚደረግ ገልጸዋል።
Seledadotio
Seledadotio
አየር መንገዱ ወደ አውስትራሊያ በረራ የመጀመር ከፍተኛ ፍላጎት እንዳለውና ገበያውም እንዳለ መረዳቱን የአየር መንገዱ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ጣሰው ተናግረዋል።
ነገር ግን አሁን ላይ ወደ አውስትራልያ በረራ ለመጀመር " አውሮፕላን የለንም " ብለዋል።
ለዚህም ረጅም ርቀት መጓዝ የሚችሉ አዳዲስ አውሮፕላኖች ግዢ እየተከናወነ መሆኑን ተጠቁሟል።
አየር መንገዱ ከጥር 2020 ዓ.ም ጀምሮ ከቦይንግ እና ኤርባስ ኩባንያዎች የሚረከባቸው በርከት ያሉ አዳዲስ አውሮፕላኖች በመኖራቸው ለአውስትራሊያው መስመር በረራ መጀመር ዝግጅት እንደሚደረግ ገልጸዋል።
Seledadotio
Seledadotio
2 days ago
የ6ኛ ክፍል ሚኒስትሪ ፈተናን 81 ትምህርት ቤቶች አንድም ተማሪ አላሳለፉም ተባለ
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ትምህርት ቢሮ የ2018 ዓ.ም የ6ኛ እና የ8ኛ ክፍል ማለፊያ ነጥብ ክልላዊ ፈተና 50 እና ከዚያ በላይ መሆኑን ገልጿል።ድጋፍ ለሚያስፈልጋቸው ደግሞ 48 እና ከዛ በላይ ማለፊያ ነጥብ ተቆርጦለታል።የ8ኛ ክፍል ፈተናን ለመውሰድ የተመዘገቡ ተማሪዎች 86 ሺህ 502 እንደሆኑ የተገለፀ ሲሆን 78 ሺህ 203 የሚሆኑት ፈተናውን ወስደዋል።
ከእነዚህ ውስጥ ወደ ቀጣይ ክፍል ያለፋት 47 ሺህ 307 ተማሪዎች መሆናቸውን የጂንካ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች የህዝብና ሚዲያ ግንኙነት ዳይሬክተር አቶ የሱፍ አህመድ ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል።በዚህም መሠረት ክልላዊ ውጤት ከመቶ አንፃር ሲታይ 60 ነጥብ 4 መሆኑ ተገልጿል።በተመሳሳይ የ6ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ለመውሰድ የተመዘገቡ ተፈታኞች 126 ሺህ 224 ናቸው። ፈተና የወሰዱት ደግሞ 110 ሺህ 566 ከእነዚህ ደግሞ ማለፊያ ነጥብ አስመዝግበው ወደ ቀጣይ 7ኛ ክፍል የተዛወሩ 70 ሺህ 584 መሆናቸውን አቶ የሱፍ ነግረውናል።
በዚህም ክልላዊ ውጤት በመቶ ሲገለፅ 63 ነጥብ 8 እንደሆነ ተገልጿል። 540 ትምህርት ቤቶች የ8ኛ ክፍል ተማሪዎቻቸውን ሙሉ በሙሉ አሳልፈዋል።በተመሳሳይ የ6ኛ ክፍል ፈተናን አስመልክቶ 476 ትምህርት ቤቶች ሙሉ በሙሉ ተማሪዎቻቸውን ሲያሳልፉ 81 ትምህርት ቤቶች ደግሞ አንድም ተማሪ አላሳለፉም።
በአጠቃላይ ክልላዊ ውጤቱ ከአምና የትምህርት ዘመን ውጤት ጋር ሲነፃፀር የ8ኛ ክፍል በ3 በመቶ ያነሰ አፈፃፀምን አስመዝግቧል ። አምና በነበረው ክልላዊ ውጤት 63 በመቶ የሆነ ውጤት ተመዝግቦበት እንደነበር ተገልጿል።በተመሳሳይ የ6ኛ ክፍል የአምና ክልላዊ ውጤትን በተመለከተ 56 በመቶ አፈፃፀም የታየበት እንደነበር የተነገረ ሲሆን በ2018 በጀት አመት ደግሞ 63 ነጥብ 84 በመቶ መሆኑን አቶ የሱፍ አህመድ ጨምረው ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል።
Seledadotio
Seledadotio
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ትምህርት ቢሮ የ2018 ዓ.ም የ6ኛ እና የ8ኛ ክፍል ማለፊያ ነጥብ ክልላዊ ፈተና 50 እና ከዚያ በላይ መሆኑን ገልጿል።ድጋፍ ለሚያስፈልጋቸው ደግሞ 48 እና ከዛ በላይ ማለፊያ ነጥብ ተቆርጦለታል።የ8ኛ ክፍል ፈተናን ለመውሰድ የተመዘገቡ ተማሪዎች 86 ሺህ 502 እንደሆኑ የተገለፀ ሲሆን 78 ሺህ 203 የሚሆኑት ፈተናውን ወስደዋል።
ከእነዚህ ውስጥ ወደ ቀጣይ ክፍል ያለፋት 47 ሺህ 307 ተማሪዎች መሆናቸውን የጂንካ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች የህዝብና ሚዲያ ግንኙነት ዳይሬክተር አቶ የሱፍ አህመድ ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል።በዚህም መሠረት ክልላዊ ውጤት ከመቶ አንፃር ሲታይ 60 ነጥብ 4 መሆኑ ተገልጿል።በተመሳሳይ የ6ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ለመውሰድ የተመዘገቡ ተፈታኞች 126 ሺህ 224 ናቸው። ፈተና የወሰዱት ደግሞ 110 ሺህ 566 ከእነዚህ ደግሞ ማለፊያ ነጥብ አስመዝግበው ወደ ቀጣይ 7ኛ ክፍል የተዛወሩ 70 ሺህ 584 መሆናቸውን አቶ የሱፍ ነግረውናል።
በዚህም ክልላዊ ውጤት በመቶ ሲገለፅ 63 ነጥብ 8 እንደሆነ ተገልጿል። 540 ትምህርት ቤቶች የ8ኛ ክፍል ተማሪዎቻቸውን ሙሉ በሙሉ አሳልፈዋል።በተመሳሳይ የ6ኛ ክፍል ፈተናን አስመልክቶ 476 ትምህርት ቤቶች ሙሉ በሙሉ ተማሪዎቻቸውን ሲያሳልፉ 81 ትምህርት ቤቶች ደግሞ አንድም ተማሪ አላሳለፉም።
በአጠቃላይ ክልላዊ ውጤቱ ከአምና የትምህርት ዘመን ውጤት ጋር ሲነፃፀር የ8ኛ ክፍል በ3 በመቶ ያነሰ አፈፃፀምን አስመዝግቧል ። አምና በነበረው ክልላዊ ውጤት 63 በመቶ የሆነ ውጤት ተመዝግቦበት እንደነበር ተገልጿል።በተመሳሳይ የ6ኛ ክፍል የአምና ክልላዊ ውጤትን በተመለከተ 56 በመቶ አፈፃፀም የታየበት እንደነበር የተነገረ ሲሆን በ2018 በጀት አመት ደግሞ 63 ነጥብ 84 በመቶ መሆኑን አቶ የሱፍ አህመድ ጨምረው ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል።
Seledadotio
Seledadotio
Sponsored by
Surafel
3 days ago
“ከምኩራቡ በስተጀርባ”፡ የቤተ-እስራኤላውያንን ስውር ታሪክ የሚያወሳው አዲስ መጽሐፍ ተመረቀ
የቤተ-እስራኤላውያንን ህይወት እና ስውር ታሪክ የሚያወሳው “ከምኩራቡ በስተጀርባ” የተሰኘው አዲስ መጽሐፍ በስቴይ ኢዚ ፕላዛ በድምቀት ተመርቋል።
በደራሲ ዶክተር ኢዮስያስ እሱንዳለ የተሰናዳው ይህ አጓጊ ሥራ፣ በኢትዮጵያ ማህበራዊ ታሪክ ውስጥ “ባለእጆች” እየተባሉ የሚጠሩትን የቤተ-እስራኤላውያን ማህበረሰብ ሕይወት፣ የደረሰባቸውን ማህበራዊ ጫና እና የማንነት ጥያቄ በልብ-ወለድ መዋቅር ውስጥ ፈትሾ ያቀርባል።
መጽሐፉ ደራሲው በዶክትሬት (PhD) ጥናታቸው ላይ ተመርኩዘው ያዘጋጁት ሲሆን፣ ታሪኩ ከአዲስ አበባው ቀጨኔ እና ጉለሌ ሰፈሮች ተነስቶ እስከ መርሃቤቴ ይዘልቃል። በዘመናዊ እውቀት የሰለጠነው አባተ የተባለ ወጣት ምሁር የሚያደርገውን ውስጣዊ የማንነት ፍለጋ፣ የቀጨኔን ምኩራብ አምልኮ እና የታሪካዊውን "ዘመቻ ሙሴ" ምስጢራዊ የስደት ውጣ ውረዶች በከፍተኛ የታሪክ መረጃዎች አስደግፎ አቅፏል።
በምርቃቱ ሥነ-ሥርዓት ላይ ደራሲው የወላጆቻቸውን የ55 ዓመት የጋብቻ ዘመን በካባ በማልበስ ያከበሩ ሲሆን፣ መጽሐፉም የአባ ቢተውና የባለቤታቸውን የ60 ዓመታት የትዳር ጽናት፣ ባህላዊ የዕራት ማዕድ ሥርዓት እና ጠንካራ የማህበረሰብ እሴቶችን ያጎላል። በተጨማሪም አባተ ከአውቶብስ ጉዞ ላይ ከተዋወቃት «ሰላም» ከተባለች ነርስ ጋር ያሳለፈውን ጥልቅ የፍቅር ታሪክ አካቷል።
የመጽሐፉ የቋንቋ አማካሪ ዶክተር ዘላለም ግርማ እንደገለጹት፤ ሥራው የቆየውን የአዲስ አበባ ሰፈር ድባብ እና ህያው የቋንቋ ዘይቤ በከፍተኛ ጥራት የጠበቀ፣ የፍትህ፣ የፍቅርና የጽናት መገለጫ የሆነ የታሪክ ሀብት ነው። መጽሐፉ እንደ «ፈ ላሻ» እና «ካይላ” ያሉ ስሞች ለዘመናት እንዴት እንደ ስ ድብ ያገለግሉ እንደነበር በመተንተን፣ በማህበረሰቡ ላይ የደረሰውን የስነ-ልቦና ጠባሳ በግልጽ ያወጣል።
በምርቃት መርሃ-ግብሩ ላይ ለማህበረሰቡ ትልቅ አስተዋጽኦ ያበረከቱ ታዋቂ ግለሰቦች የተገኙ ሲሆን፣ ከእነሱም መካከል ደራሲና ገጣሚ ከፈለኝ ዘለለው፣ መጋቢ ዶክተር ሰለሺ ከበደ፣ የህክምና ድጋፍ አስተባባሪዋ ወ/ሮ ዘነበች እና የማህበረሰብ ተወካዩ አባ እሸቱ ይገኙበታል። እንዲሁም በልማት ስራዎች የተሰማሩት አቶ ሰለሞን አሰፋ፣ መጋቢ ደምስ ማሞ እና የሰሊሆም ድርጅት መስራች ወጣት ሚኪያስ ለገሰ ታድመዋል።
የጽሑፉ ገምጋሚዎች እንዳመለከቱት፣ መጽሐፉ እውነተኛ ታሪክን ከልብ ወለድ ትረካ ጋር አዋህዶ ማቀረቡ ለአንባቢው ሳቢና ቀልብ ገዢ ያደርገዋል። ፀሐፊው በማህበረሰባዊ መገለልና በማንነት ክፍፍል ላይ የነበረውን አመለካከት በመቃወም፣ በእውቀት እና በጽናት ላይ የተመሰረተ ማህበራዊ ፍትህ እንዲሰፍን ጥሪ ያቀርባል።
በአጠቃላይ “ከምኩራቡ በስተጀርባ” መጽሐፍ ለዘመናት ተሸፍነው የቆዩ ታሪካዊ እውነታዎችን፣ የስደት ጉዞዎችን እና የማህበረሰቡን ሃይማኖታዊና ባህላዊ አደራ ለትውልድ የሚያስተላልፍ ውድ ቅርጽ ሆኖ ለአንባቢያን ተበርክቷል።
የቤተ-እስራኤላውያንን ህይወት እና ስውር ታሪክ የሚያወሳው “ከምኩራቡ በስተጀርባ” የተሰኘው አዲስ መጽሐፍ በስቴይ ኢዚ ፕላዛ በድምቀት ተመርቋል።
በደራሲ ዶክተር ኢዮስያስ እሱንዳለ የተሰናዳው ይህ አጓጊ ሥራ፣ በኢትዮጵያ ማህበራዊ ታሪክ ውስጥ “ባለእጆች” እየተባሉ የሚጠሩትን የቤተ-እስራኤላውያን ማህበረሰብ ሕይወት፣ የደረሰባቸውን ማህበራዊ ጫና እና የማንነት ጥያቄ በልብ-ወለድ መዋቅር ውስጥ ፈትሾ ያቀርባል።
መጽሐፉ ደራሲው በዶክትሬት (PhD) ጥናታቸው ላይ ተመርኩዘው ያዘጋጁት ሲሆን፣ ታሪኩ ከአዲስ አበባው ቀጨኔ እና ጉለሌ ሰፈሮች ተነስቶ እስከ መርሃቤቴ ይዘልቃል። በዘመናዊ እውቀት የሰለጠነው አባተ የተባለ ወጣት ምሁር የሚያደርገውን ውስጣዊ የማንነት ፍለጋ፣ የቀጨኔን ምኩራብ አምልኮ እና የታሪካዊውን "ዘመቻ ሙሴ" ምስጢራዊ የስደት ውጣ ውረዶች በከፍተኛ የታሪክ መረጃዎች አስደግፎ አቅፏል።
በምርቃቱ ሥነ-ሥርዓት ላይ ደራሲው የወላጆቻቸውን የ55 ዓመት የጋብቻ ዘመን በካባ በማልበስ ያከበሩ ሲሆን፣ መጽሐፉም የአባ ቢተውና የባለቤታቸውን የ60 ዓመታት የትዳር ጽናት፣ ባህላዊ የዕራት ማዕድ ሥርዓት እና ጠንካራ የማህበረሰብ እሴቶችን ያጎላል። በተጨማሪም አባተ ከአውቶብስ ጉዞ ላይ ከተዋወቃት «ሰላም» ከተባለች ነርስ ጋር ያሳለፈውን ጥልቅ የፍቅር ታሪክ አካቷል።
የመጽሐፉ የቋንቋ አማካሪ ዶክተር ዘላለም ግርማ እንደገለጹት፤ ሥራው የቆየውን የአዲስ አበባ ሰፈር ድባብ እና ህያው የቋንቋ ዘይቤ በከፍተኛ ጥራት የጠበቀ፣ የፍትህ፣ የፍቅርና የጽናት መገለጫ የሆነ የታሪክ ሀብት ነው። መጽሐፉ እንደ «ፈ ላሻ» እና «ካይላ” ያሉ ስሞች ለዘመናት እንዴት እንደ ስ ድብ ያገለግሉ እንደነበር በመተንተን፣ በማህበረሰቡ ላይ የደረሰውን የስነ-ልቦና ጠባሳ በግልጽ ያወጣል።
በምርቃት መርሃ-ግብሩ ላይ ለማህበረሰቡ ትልቅ አስተዋጽኦ ያበረከቱ ታዋቂ ግለሰቦች የተገኙ ሲሆን፣ ከእነሱም መካከል ደራሲና ገጣሚ ከፈለኝ ዘለለው፣ መጋቢ ዶክተር ሰለሺ ከበደ፣ የህክምና ድጋፍ አስተባባሪዋ ወ/ሮ ዘነበች እና የማህበረሰብ ተወካዩ አባ እሸቱ ይገኙበታል። እንዲሁም በልማት ስራዎች የተሰማሩት አቶ ሰለሞን አሰፋ፣ መጋቢ ደምስ ማሞ እና የሰሊሆም ድርጅት መስራች ወጣት ሚኪያስ ለገሰ ታድመዋል።
የጽሑፉ ገምጋሚዎች እንዳመለከቱት፣ መጽሐፉ እውነተኛ ታሪክን ከልብ ወለድ ትረካ ጋር አዋህዶ ማቀረቡ ለአንባቢው ሳቢና ቀልብ ገዢ ያደርገዋል። ፀሐፊው በማህበረሰባዊ መገለልና በማንነት ክፍፍል ላይ የነበረውን አመለካከት በመቃወም፣ በእውቀት እና በጽናት ላይ የተመሰረተ ማህበራዊ ፍትህ እንዲሰፍን ጥሪ ያቀርባል።
በአጠቃላይ “ከምኩራቡ በስተጀርባ” መጽሐፍ ለዘመናት ተሸፍነው የቆዩ ታሪካዊ እውነታዎችን፣ የስደት ጉዞዎችን እና የማህበረሰቡን ሃይማኖታዊና ባህላዊ አደራ ለትውልድ የሚያስተላልፍ ውድ ቅርጽ ሆኖ ለአንባቢያን ተበርክቷል።
3 days ago
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የ6ኛ እና የ8ኛ ክፍል ፈተና ውጤት ይፋ ሆነ
📌 የ6ኛ ክፍል ውጤቱ ከባለፈው አመት ጋር ሲነጻጸር የተሻለ ነው
#ethiopia |የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ትምህርት ቢሮ የ2018 ዓ.ም የ6ኛ እና የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ውጤትን አስመልክቶ ለጋዜጠኞች በሰጠው መግለጫ ይፋ አድርጓል።
የቢሮው ኃላፊ አቶ አብዮት ደምሴ እንደገለጹት፣ የዘንድሮው ማለፊያ ነጥብ ለሁለቱም ክፍሎች ክልላዊ 50 እና ከዚያ በላይ እንዲሆን የተወሰነ ሲሆን፣ ልዩ ድጋፍ ለሚሹ አካባቢዎች ደግሞ 48 እና ከዚያ በላይ እንዲሆን ተደርጓል።
በዚህም መሠረት በ8ኛ ክፍል ፈተናውን ለመውሰድ ከተመዘገቡት 86 ሺህ 502 ተማሪዎች መካከል 78 ሺህ 203 የሚሆኑት ተፈትነው 47 ሺህ 307 ተማሪዎች ማለፊያ ነጥቡን በማስመዝገብ ወደ ቀጣይ ክፍል ተዛውረዋል።
ይህም የክልሉን አጠቃላይ የማለፍ ምጣኔ 60.4 በመቶ የሚያደርሰው ሲሆን፣ ከአምናው የ63 በመቶ ውጤት ጋር ሲነፃፀር የ3 በመቶ ቅናሽ አሳይቷል።
በተቃራኒው በ6ኛ ክፍል ከተፈተኑት 110 ሺህ 566 ተማሪዎች ውስጥ 70 ሺህ 584ቱ ማለፊያ ነጥብ በማምጣት ያለፉ ሲሆን፣ የክልሉ የማለፍ ምጣኔ 63.8 በመቶ ሆኖ ተመዝግቧል። ይህ ውጤት ከአምናው የ56 በመቶ አፈፃፀም ጋር ሲነፃፀር ከፍተኛ እድገት የታየበት ነው።
ከትምህርት ቤቶች አፈፃፀም አኳያም በ8ኛ ክፍል 540 ትምህርት ቤቶች ሙሉ በሙሉ ተማሪዎቻቸውን ማሳለፍ ሲችሉ፣ 155 ትምህርት ቤቶች ግን አንድም ተማሪ ማሳለፍ አልቻሉም።
በ6ኛ ክፍል ደግሞ 476 ትምህርት ቤቶች 100 በመቶ የማሳለፍ ስኬት ሲያስመዘግቡ፣ 81 ትምህርት ቤቶች ምንም ተማሪ ሳያሳልፉ ቀርተዋል።
የክልል ትምህርት ቢሮ
#southethiopia #ethiopiaeducation #ministryofeducation #grade8exam #grade6exam
📌 የ6ኛ ክፍል ውጤቱ ከባለፈው አመት ጋር ሲነጻጸር የተሻለ ነው
#ethiopia |የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ትምህርት ቢሮ የ2018 ዓ.ም የ6ኛ እና የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ውጤትን አስመልክቶ ለጋዜጠኞች በሰጠው መግለጫ ይፋ አድርጓል።
የቢሮው ኃላፊ አቶ አብዮት ደምሴ እንደገለጹት፣ የዘንድሮው ማለፊያ ነጥብ ለሁለቱም ክፍሎች ክልላዊ 50 እና ከዚያ በላይ እንዲሆን የተወሰነ ሲሆን፣ ልዩ ድጋፍ ለሚሹ አካባቢዎች ደግሞ 48 እና ከዚያ በላይ እንዲሆን ተደርጓል።
በዚህም መሠረት በ8ኛ ክፍል ፈተናውን ለመውሰድ ከተመዘገቡት 86 ሺህ 502 ተማሪዎች መካከል 78 ሺህ 203 የሚሆኑት ተፈትነው 47 ሺህ 307 ተማሪዎች ማለፊያ ነጥቡን በማስመዝገብ ወደ ቀጣይ ክፍል ተዛውረዋል።
ይህም የክልሉን አጠቃላይ የማለፍ ምጣኔ 60.4 በመቶ የሚያደርሰው ሲሆን፣ ከአምናው የ63 በመቶ ውጤት ጋር ሲነፃፀር የ3 በመቶ ቅናሽ አሳይቷል።
በተቃራኒው በ6ኛ ክፍል ከተፈተኑት 110 ሺህ 566 ተማሪዎች ውስጥ 70 ሺህ 584ቱ ማለፊያ ነጥብ በማምጣት ያለፉ ሲሆን፣ የክልሉ የማለፍ ምጣኔ 63.8 በመቶ ሆኖ ተመዝግቧል። ይህ ውጤት ከአምናው የ56 በመቶ አፈፃፀም ጋር ሲነፃፀር ከፍተኛ እድገት የታየበት ነው።
ከትምህርት ቤቶች አፈፃፀም አኳያም በ8ኛ ክፍል 540 ትምህርት ቤቶች ሙሉ በሙሉ ተማሪዎቻቸውን ማሳለፍ ሲችሉ፣ 155 ትምህርት ቤቶች ግን አንድም ተማሪ ማሳለፍ አልቻሉም።
በ6ኛ ክፍል ደግሞ 476 ትምህርት ቤቶች 100 በመቶ የማሳለፍ ስኬት ሲያስመዘግቡ፣ 81 ትምህርት ቤቶች ምንም ተማሪ ሳያሳልፉ ቀርተዋል።
የክልል ትምህርት ቢሮ
#southethiopia #ethiopiaeducation #ministryofeducation #grade8exam #grade6exam
3 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) አንበሳ ባንክ በሚቀጥለው ወር የሚያደርገውን ምርጫ ተከትሎ ሽኩቻ እየተደረገ ነው፡፡ በአንበሳ ባንክ ውስጥ የተፈጠረው አለመግባባት አሁንም መቀጠሉን ምንጮች ይናገራሉ፡፡ ለውዝግቡ መንስኤ የሆነው ባለፉት ወራት በአዲስ አበባ ውስጥ የሚገኙ ግለሰቦችና ኩባንያዎች በባንኩ ቦርድና ማኔጅመንት ላይ ጫና በማሳደር ብድር እንዲሰጣቸው መጠየቃቸው መሆኑን የሚናገሩት ምንጮቹ ብድሩን ባለማግኘታቸው አመራሩን የማንሳት ጥረት ማድረግ መጀመራቸውን ያስረዳሉ፡፡
ይህንን ተከትሎ ‹‹ጉዳዩ ህጋዊ እንዲመስል›› ለብሄራዊ ባንክ ህገ ወጥ አሰራርንና ምርጫ ማጭበርበርን የተመለከቱ ጥቆማዎችን መስጠታቸውን አውስተዋል፡፡ ብሄራዊ ባንክ በቀረበው መረጃ ላይ ምርመራ አድርጎ ህገ ወጥ አሰራር አለማግኘቱን ቢያስታውቅም በሚቀጥለው ወር የባንኩ ጠቅላላ ጉባኤ ተጠርቶ አዲስ አመራር ምርጫ እንዲካሄድ ውሳኔ ማሳለፉ የሚታወስ ነው፡፡
ምንጮቹ እንደሚሉት ይህ ምርጫ ከመካሄዱ በፊት በማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ ሽኩቻው አይሎ ይታያል፡፡ በአንድ ወገን የፕሬዝደንቱ አቶ ዳንኤል ተከስተ ደጋፊዎች አመራራቸውን ለማስቀጠል ዘመቻ በማድረግ ላይ ሲሆኑ በሌላ ወገን ደግሞ የቦርድ አባል በሆኑት ዶክተር አክሊሉ ገብረስላሴ የሚመራው አካል ደግሞ አመራሩን ለማንሳት ሌላ ዘመቻ እያደረገ ይገኛል፡፡
እንደምንጮቹ ከሆነ ይህ በአንበሳ ባንክ ውስጥ የተፈጠረው ትርምስ ፖለቲካዊ እንድምታ ያለው ከመሆኑም በላይ ከህወሀት ክፍፍል ጋር የተያያዘ ነው፡፡ ምንጮቹ እንደሚሉት የባንኩ ባለአክስዮኖች በሚቀጥለው ወር በሚካሄደው ምርጫ ለባንኩ ህልውና ሲሉ ጥንቃቄ የታከለበት ውሳኔ መስጠት ይገባቸዋል፡፡ እንዲሁም ብሄራዊ ባንክ በተመሳሳይ ለጉዳዩ ተገቢውን ትኩረት ሰጥቶ ፍትሀዊ ፍርድ መስጠት እንዳለበትም አሳስበዋል፡፡
ይህንን ተከትሎ ‹‹ጉዳዩ ህጋዊ እንዲመስል›› ለብሄራዊ ባንክ ህገ ወጥ አሰራርንና ምርጫ ማጭበርበርን የተመለከቱ ጥቆማዎችን መስጠታቸውን አውስተዋል፡፡ ብሄራዊ ባንክ በቀረበው መረጃ ላይ ምርመራ አድርጎ ህገ ወጥ አሰራር አለማግኘቱን ቢያስታውቅም በሚቀጥለው ወር የባንኩ ጠቅላላ ጉባኤ ተጠርቶ አዲስ አመራር ምርጫ እንዲካሄድ ውሳኔ ማሳለፉ የሚታወስ ነው፡፡
ምንጮቹ እንደሚሉት ይህ ምርጫ ከመካሄዱ በፊት በማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ ሽኩቻው አይሎ ይታያል፡፡ በአንድ ወገን የፕሬዝደንቱ አቶ ዳንኤል ተከስተ ደጋፊዎች አመራራቸውን ለማስቀጠል ዘመቻ በማድረግ ላይ ሲሆኑ በሌላ ወገን ደግሞ የቦርድ አባል በሆኑት ዶክተር አክሊሉ ገብረስላሴ የሚመራው አካል ደግሞ አመራሩን ለማንሳት ሌላ ዘመቻ እያደረገ ይገኛል፡፡
እንደምንጮቹ ከሆነ ይህ በአንበሳ ባንክ ውስጥ የተፈጠረው ትርምስ ፖለቲካዊ እንድምታ ያለው ከመሆኑም በላይ ከህወሀት ክፍፍል ጋር የተያያዘ ነው፡፡ ምንጮቹ እንደሚሉት የባንኩ ባለአክስዮኖች በሚቀጥለው ወር በሚካሄደው ምርጫ ለባንኩ ህልውና ሲሉ ጥንቃቄ የታከለበት ውሳኔ መስጠት ይገባቸዋል፡፡ እንዲሁም ብሄራዊ ባንክ በተመሳሳይ ለጉዳዩ ተገቢውን ትኩረት ሰጥቶ ፍትሀዊ ፍርድ መስጠት እንዳለበትም አሳስበዋል፡፡
3 days ago
ከምኩራቡ በስተጀርባ
#ethiopia | የቤተ እስራኤላዊያንን ስውር ታሪክ የሚያወሳው መጽሐፍ ተመረቀ።
በደራሲ ዶክተር ኢዮስያስ እሱንዳለ የተሰናዳው ይህ አጓጊ ሥራ፣ በኢትዮጵያ ማህበራዊ ታሪክ ውስጥ “ባለእጆች”እየተባሉ የሚጠሩትን የቤተ-እስራኤላውያን ማህበረሰብ ሕይወት፣ የደረሰባቸውን ማህበራዊ ጫና እና የማንነት ጥያቄ በልብ-ወለድ መዋቅር ውስጥ ፈትሾ ያቀርባል።
መጽሐፉ ደራሲው በዶክትሬት (PhD) ጥናታቸው ላይ ተመርኩዘው ያዘጋጁት ሲሆን፣ ታሪኩ ከአዲስ አበባው ቀጨኔ እና ጉለሌ ሰፈሮች ተነስቶ እስከ መርሃቤቴ ይዘልቃል።
በዘመናዊ እውቀት የሰለጠነው አባተ የተባለ ወጣት ምሁር የሚያደርገውን ውስጣዊ የማንነት ፍለጋ፣ የቀጨኔን ምኩራብ አምልኮ እና የታሪካዊውን "ዘመቻ ሙሴ" ምስጢራዊ የስደት ውጣ ውረዶች በከፍተኛ የታሪክ መረጃዎች አስደግፎ አቅፏል።
በምርቃቱ ሥነ-ሥርዓት ላይ ደራሲው የወላጆቻቸውን የ55 ዓመት የጋብቻ ዘመን በካባ በማልበስ ያከበሩ ሲሆን፣ መጽሐፉም የአባ ቢተውና የባለቤታቸውን የ60 ዓመታት የትዳር ጽናት፣ ባህላዊ የዕራት ማዕድ ሥርዓት እና ጠንካራ የማህበረሰብ እሴቶችን ያጎላል።
በተጨማሪም አባተ ከአውቶብስ ጉዞ ላይ ከተዋወቃት «ሰላም» ከተባለች ነርስ ጋር ያሳለፈውን ጥልቅ የፍቅር ታሪክ አካቷል።
የመጽሐፉ የቋንቋ አማካሪ ዶክተር ዘላለም ግርማ እንደገለጹት፤ ሥራው የቆየውን የአዲስ አበባ ሰፈር ድባብ እና ህያው የቋንቋ ዘይቤ በከፍተኛ ጥራት የጠበቀ፣ የፍትህ፣ የፍቅርና የጽናት መገለጫ የሆነ የታሪክ ሀብት ነው።
መጽሐፉ እንደ «ፈላሻ» እና «ካይላ” ያሉ ስሞች ለዘመናት እንዴት እንደ ስድብ ያገለግሉ እንደነበር በመተንተን፣ በማህበረሰቡ ላይ የደረሰውን የስነ-ልቦና ጠባሳ በግልጽ ያወጣል።
በምርቃት መርሃ-ግብሩ ላይ ለማህበረሰቡ ትልቅ አስተዋጽኦ ያበረከቱ ታዋቂ ግለሰቦች የተገኙ ሲሆን፣ ከእነሱም መካከል ደራሲና ገጣሚ ከፈለኝ ዘለለው፣ መጋቢ ዶክተር ሰለሺ ከበደ፣ የህክምና ድጋፍ አስተባባሪዋ ወ/ሮ ዘነበች እና የማህበረሰብ ተወካዩ አባ እሸቱ ይገኙበታል።
እንዲሁም በልማት ስራዎች የተሰማሩት አቶ ሰለሞን አሰፋ፣ መጋቢ ደምስ ማሞ እና የሰሊሆም ድርጅት መስራች ወጣት ሚኪያስ ለገሰ ታድመዋል።
የጽሑፉ ገምጋሚዎች እንዳመለከቱት፣ መጽሐፉ እውነተኛ ታሪክን ከልብ ወለድ ትረካ ጋር አዋህዶ ማቀረቡ ለአንባቢው ሳቢና ቀልብ ገዢ ያደርገዋል።
ፀሐፊው በማህበረሰባዊ መገለልና በማንነት ክፍፍል ላይ የነበረውን አመለካከት በመቃወም፣ በእውቀት እና በጽናት ላይ የተመሰረተ ማህበራዊ ፍትህ እንዲሰፍን ጥሪ ያቀርባል።
በአጠቃላይ “ከምኩራቡ በስተጀርባ” መጽሐፍ ለዘመናት ተሸፍነው የቆዩ ታሪካዊ እውነታዎችን፣ የስደት ጉዞዎችን እና የማህበረሰቡን ሃይማኖታዊና ባህላዊ አደራ ለትውልድ የሚያስተላልፍ ውድ ቅርጽ ሆኖ ለአንባቢያን ተበርክቷል።
ሔኖክ ወ/ገብርኤል
#ethiopia #getutemesgen #getunews
#ethiopia | የቤተ እስራኤላዊያንን ስውር ታሪክ የሚያወሳው መጽሐፍ ተመረቀ።
በደራሲ ዶክተር ኢዮስያስ እሱንዳለ የተሰናዳው ይህ አጓጊ ሥራ፣ በኢትዮጵያ ማህበራዊ ታሪክ ውስጥ “ባለእጆች”እየተባሉ የሚጠሩትን የቤተ-እስራኤላውያን ማህበረሰብ ሕይወት፣ የደረሰባቸውን ማህበራዊ ጫና እና የማንነት ጥያቄ በልብ-ወለድ መዋቅር ውስጥ ፈትሾ ያቀርባል።
መጽሐፉ ደራሲው በዶክትሬት (PhD) ጥናታቸው ላይ ተመርኩዘው ያዘጋጁት ሲሆን፣ ታሪኩ ከአዲስ አበባው ቀጨኔ እና ጉለሌ ሰፈሮች ተነስቶ እስከ መርሃቤቴ ይዘልቃል።
በዘመናዊ እውቀት የሰለጠነው አባተ የተባለ ወጣት ምሁር የሚያደርገውን ውስጣዊ የማንነት ፍለጋ፣ የቀጨኔን ምኩራብ አምልኮ እና የታሪካዊውን "ዘመቻ ሙሴ" ምስጢራዊ የስደት ውጣ ውረዶች በከፍተኛ የታሪክ መረጃዎች አስደግፎ አቅፏል።
በምርቃቱ ሥነ-ሥርዓት ላይ ደራሲው የወላጆቻቸውን የ55 ዓመት የጋብቻ ዘመን በካባ በማልበስ ያከበሩ ሲሆን፣ መጽሐፉም የአባ ቢተውና የባለቤታቸውን የ60 ዓመታት የትዳር ጽናት፣ ባህላዊ የዕራት ማዕድ ሥርዓት እና ጠንካራ የማህበረሰብ እሴቶችን ያጎላል።
በተጨማሪም አባተ ከአውቶብስ ጉዞ ላይ ከተዋወቃት «ሰላም» ከተባለች ነርስ ጋር ያሳለፈውን ጥልቅ የፍቅር ታሪክ አካቷል።
የመጽሐፉ የቋንቋ አማካሪ ዶክተር ዘላለም ግርማ እንደገለጹት፤ ሥራው የቆየውን የአዲስ አበባ ሰፈር ድባብ እና ህያው የቋንቋ ዘይቤ በከፍተኛ ጥራት የጠበቀ፣ የፍትህ፣ የፍቅርና የጽናት መገለጫ የሆነ የታሪክ ሀብት ነው።
መጽሐፉ እንደ «ፈላሻ» እና «ካይላ” ያሉ ስሞች ለዘመናት እንዴት እንደ ስድብ ያገለግሉ እንደነበር በመተንተን፣ በማህበረሰቡ ላይ የደረሰውን የስነ-ልቦና ጠባሳ በግልጽ ያወጣል።
በምርቃት መርሃ-ግብሩ ላይ ለማህበረሰቡ ትልቅ አስተዋጽኦ ያበረከቱ ታዋቂ ግለሰቦች የተገኙ ሲሆን፣ ከእነሱም መካከል ደራሲና ገጣሚ ከፈለኝ ዘለለው፣ መጋቢ ዶክተር ሰለሺ ከበደ፣ የህክምና ድጋፍ አስተባባሪዋ ወ/ሮ ዘነበች እና የማህበረሰብ ተወካዩ አባ እሸቱ ይገኙበታል።
እንዲሁም በልማት ስራዎች የተሰማሩት አቶ ሰለሞን አሰፋ፣ መጋቢ ደምስ ማሞ እና የሰሊሆም ድርጅት መስራች ወጣት ሚኪያስ ለገሰ ታድመዋል።
የጽሑፉ ገምጋሚዎች እንዳመለከቱት፣ መጽሐፉ እውነተኛ ታሪክን ከልብ ወለድ ትረካ ጋር አዋህዶ ማቀረቡ ለአንባቢው ሳቢና ቀልብ ገዢ ያደርገዋል።
ፀሐፊው በማህበረሰባዊ መገለልና በማንነት ክፍፍል ላይ የነበረውን አመለካከት በመቃወም፣ በእውቀት እና በጽናት ላይ የተመሰረተ ማህበራዊ ፍትህ እንዲሰፍን ጥሪ ያቀርባል።
በአጠቃላይ “ከምኩራቡ በስተጀርባ” መጽሐፍ ለዘመናት ተሸፍነው የቆዩ ታሪካዊ እውነታዎችን፣ የስደት ጉዞዎችን እና የማህበረሰቡን ሃይማኖታዊና ባህላዊ አደራ ለትውልድ የሚያስተላልፍ ውድ ቅርጽ ሆኖ ለአንባቢያን ተበርክቷል።
ሔኖክ ወ/ገብርኤል
#ethiopia #getutemesgen #getunews
Sponsored by
Surafel
3 days ago
የቢሾፍቱ አውሮፕላን ማረፊያ ፕሮጀክት ኢትዮጵያ በአቪየሽን ዘርፍ መሪነቷን እንደታጠናክር ያስችላታል - ሲኤንኤን
***********************
የዓለማችን ታዋቂው የዜና መረብ ሲኤንኤን (CNN) "ኮኔክቲንግ አፍሪካ" በተሰኘው ዝነኛ ፕሮግራሙ፣ የአፍሪካ የአቪዬሽን መሪ የሆነው የኢትዮጵያ አየር መንገድ እየመራው ያለውን ታላቅ የመሠረተ ልማት፣ የኢኮኖሚ እና የቱሪዝም እምርታ በሰፊው ዳስሷል።
ዘገባው እንደ አመላከተው፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ለአህጉሪቱ ምሳሌ የሚሆን የዕድገት ሞተር ከመሆኑም በላይ ኢትዮጵያን የዓለም አቀፍ ትስስር ማዕከል በማድረግ ረገድ ወደ አዲስ እየተሸጋገረ ይገኛል።
ዘገባው ኢትዮጵያ የአቪዬሽን ዘርፏን ዘመናዊ በማድረግ፣ የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣናን (AfCFTA) ተግባራዊነት በማፋጠን እና የተፈጥሮ ሀብቶቿን ለዓለም አስተዋውቃ የቱሪዝም አቅሟን በመገንባት በኩል እያከናወነቻቸው ያሉትን ዐበይት ተግባራት በስፋት አሳይቷል።
በዘገባው ጎልተው ከተካተቱት ዐበይት ጉዳዮች መካከል በ12.5 ቢሊዮን ዶላር ወጪ ግንባታው የተጀመረው እና በአፍሪካ ታሪክ ትልቁ የሆነው የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሜጋ ፕሮጀክት ቀዳሚው ነው።
ይህ ዘመናዊ የአቪዬሽን መንደር የመጀመሪያው ምዕራፍ ሲጠናቀቅ 60 ሚሊዮን፣ ሙሉ በሙሉ ሲጠናቀቅ ደግሞ በዓመት እስከ 110 ሚሊዮን መንገደኞችን የማስተናገድ እና 4 ሚሊዮን ቶን ካርጎ የማጓጓዝ ከፍተኛ አቅም ይኖረዋል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ መስፍን ጣሰው ከሲኤንኤን ዘጋቢ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ፣ አዲሱ አውሮፕላን ማረፊያ አፍሪካውያንን እርስ በእርስ በማስተሳሰር ረገድ የመሪነት ሚናውን እንደሚቀጥል ገልጸዋል።
በተጨማሪም አየር መንገዱ የአፍሪካ ነፃ ንግድ ቀጣናን ስኬታማ ለማድረግ እና አህጉራዊ የንግድ ትስስርን ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር ቁልፍ ሞተር መሆኑን አስረድተዋል።
በዘገባው ላይ እንደተጠቆመው የኢትዮጵያን ተፈጥሯዊና ታሪካዊ ሀብቶች ለዓለም አቀፍ እና ለአህጉራችን ጎብኚዎች ተደራሽ ለማድረግ ዘመናዊ የመሠረተ ልማት ግንባታዎች፣ ደረጃቸውን የጠበቁ የማረፊያ ስፍራዎች እና አዳዲስ የመንገድ ዝርጋታዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ።
ይህም ኢትዮጵያ ከቱሪዝም ዘርፍ የምታገኘውን የኢኮኖሚ ጥቅም ወደ ላቀ ደረጃ የሚያሸጋግር ነው።
የሲኤንኤን ዘገባ የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአቪዬሽን ዘርፍ እያመጣ ያለውን ብሩህ ተስፋ እና በአቪዬሽን መሠረተ ልማት አህጉራዊ መሪነቷን በጽኑ የምታረጋግጥበትን የልማት ጉዞ በግልጽ ያሳየ ነው።
የአፍሪካ ኩራት የሆነው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ሀገራችን የአህጉሪቱ ዋና የንግድ፣ የቱሪዝም እና የኢኮኖሚ መገናኛ ማዕከል በማድረግ ጉዞውን አጠናክሮ ቀጥሏል።
በሔዋን ጌታቸው
#ethiopia #ebc #bishoftuairport #ethiopianairlines #connectingafrica #cnn
***********************
የዓለማችን ታዋቂው የዜና መረብ ሲኤንኤን (CNN) "ኮኔክቲንግ አፍሪካ" በተሰኘው ዝነኛ ፕሮግራሙ፣ የአፍሪካ የአቪዬሽን መሪ የሆነው የኢትዮጵያ አየር መንገድ እየመራው ያለውን ታላቅ የመሠረተ ልማት፣ የኢኮኖሚ እና የቱሪዝም እምርታ በሰፊው ዳስሷል።
ዘገባው እንደ አመላከተው፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ለአህጉሪቱ ምሳሌ የሚሆን የዕድገት ሞተር ከመሆኑም በላይ ኢትዮጵያን የዓለም አቀፍ ትስስር ማዕከል በማድረግ ረገድ ወደ አዲስ እየተሸጋገረ ይገኛል።
ዘገባው ኢትዮጵያ የአቪዬሽን ዘርፏን ዘመናዊ በማድረግ፣ የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣናን (AfCFTA) ተግባራዊነት በማፋጠን እና የተፈጥሮ ሀብቶቿን ለዓለም አስተዋውቃ የቱሪዝም አቅሟን በመገንባት በኩል እያከናወነቻቸው ያሉትን ዐበይት ተግባራት በስፋት አሳይቷል።
በዘገባው ጎልተው ከተካተቱት ዐበይት ጉዳዮች መካከል በ12.5 ቢሊዮን ዶላር ወጪ ግንባታው የተጀመረው እና በአፍሪካ ታሪክ ትልቁ የሆነው የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሜጋ ፕሮጀክት ቀዳሚው ነው።
ይህ ዘመናዊ የአቪዬሽን መንደር የመጀመሪያው ምዕራፍ ሲጠናቀቅ 60 ሚሊዮን፣ ሙሉ በሙሉ ሲጠናቀቅ ደግሞ በዓመት እስከ 110 ሚሊዮን መንገደኞችን የማስተናገድ እና 4 ሚሊዮን ቶን ካርጎ የማጓጓዝ ከፍተኛ አቅም ይኖረዋል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ መስፍን ጣሰው ከሲኤንኤን ዘጋቢ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ፣ አዲሱ አውሮፕላን ማረፊያ አፍሪካውያንን እርስ በእርስ በማስተሳሰር ረገድ የመሪነት ሚናውን እንደሚቀጥል ገልጸዋል።
በተጨማሪም አየር መንገዱ የአፍሪካ ነፃ ንግድ ቀጣናን ስኬታማ ለማድረግ እና አህጉራዊ የንግድ ትስስርን ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር ቁልፍ ሞተር መሆኑን አስረድተዋል።
በዘገባው ላይ እንደተጠቆመው የኢትዮጵያን ተፈጥሯዊና ታሪካዊ ሀብቶች ለዓለም አቀፍ እና ለአህጉራችን ጎብኚዎች ተደራሽ ለማድረግ ዘመናዊ የመሠረተ ልማት ግንባታዎች፣ ደረጃቸውን የጠበቁ የማረፊያ ስፍራዎች እና አዳዲስ የመንገድ ዝርጋታዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ።
ይህም ኢትዮጵያ ከቱሪዝም ዘርፍ የምታገኘውን የኢኮኖሚ ጥቅም ወደ ላቀ ደረጃ የሚያሸጋግር ነው።
የሲኤንኤን ዘገባ የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአቪዬሽን ዘርፍ እያመጣ ያለውን ብሩህ ተስፋ እና በአቪዬሽን መሠረተ ልማት አህጉራዊ መሪነቷን በጽኑ የምታረጋግጥበትን የልማት ጉዞ በግልጽ ያሳየ ነው።
የአፍሪካ ኩራት የሆነው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ሀገራችን የአህጉሪቱ ዋና የንግድ፣ የቱሪዝም እና የኢኮኖሚ መገናኛ ማዕከል በማድረግ ጉዞውን አጠናክሮ ቀጥሏል።
በሔዋን ጌታቸው
#ethiopia #ebc #bishoftuairport #ethiopianairlines #connectingafrica #cnn
3 days ago
በውጭ ሀገር ለሚኖሩ ኢትዮጵያውያን የኤሌክትሮኒክስ ፓስፖርት አገልግሎት በቅርቡ እንደሚጀመር ተነገረ
የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት በውጭ ሀገራት ለሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ምቹ አሰራሮችን እየዘረጋ መሆኑን አስታውቋል።
ከእነዚህም መካከል አዲሱ የኤሌክትሮኒክስ ፓስፖርት አገልግሎት በኤምባሲዎችና በቆንስላዎች በኩል በቅርቡ እንደሚጀመር ገልጿል።
የኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት ህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር አቶ አምቦ መቃሳ እንደገለጹት፥ለዲያስፖራው የሚሰጠው አገልግሎት እንዲቀላጠፍ አዲስ ድረ-ገጽ ተዘጋጅቷል።
ይህ ድረ-ገጽ ተገልጋዮች ባሉበት ሀገር ሳይገደቡ የፓስፖርት እድሳትና ሌሎች ተያያዥ ጉዳዮችን በቀላሉ እንዲያከናውኑ የሚያስችል ነው ብለዋል።
የቢጫ ካርድ ባለቤቶች ቀደም ሲልም በሀገር ውስጥ ኢንቨስት የማድረግና የመንቀሳቀስ መብት ያላቸው በመሆኑ፤አዲሱ የጎልደን ቪዛ የግድ አስፈላጊ ላይሆን እንደሚችል ተጠቁሟል።
እነዚህ ቅርንጫፎች በሁሉም የሀገሪቱ ክፍሎች የሚገኙ በመሆናቸው፣ ተገልጋዮች ወደ አዲስ አበባ ሳይመጡ በአቅራቢያቸው አገልግሎት እንዲያገኙ ያስችላቸዋል ተብሏል።
ከፓስፖርት ባለፈም፣ የነዋሪነት ፈቃድና የቪዛ አገልግሎቶች ሙሉ በሙሉ በዲጂታል መንገድ እየተሰጡ ይገኛሉ ብለዋል።
Seledadotio
Seledadotio
የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት በውጭ ሀገራት ለሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ምቹ አሰራሮችን እየዘረጋ መሆኑን አስታውቋል።
ከእነዚህም መካከል አዲሱ የኤሌክትሮኒክስ ፓስፖርት አገልግሎት በኤምባሲዎችና በቆንስላዎች በኩል በቅርቡ እንደሚጀመር ገልጿል።
የኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት ህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር አቶ አምቦ መቃሳ እንደገለጹት፥ለዲያስፖራው የሚሰጠው አገልግሎት እንዲቀላጠፍ አዲስ ድረ-ገጽ ተዘጋጅቷል።
ይህ ድረ-ገጽ ተገልጋዮች ባሉበት ሀገር ሳይገደቡ የፓስፖርት እድሳትና ሌሎች ተያያዥ ጉዳዮችን በቀላሉ እንዲያከናውኑ የሚያስችል ነው ብለዋል።
የቢጫ ካርድ ባለቤቶች ቀደም ሲልም በሀገር ውስጥ ኢንቨስት የማድረግና የመንቀሳቀስ መብት ያላቸው በመሆኑ፤አዲሱ የጎልደን ቪዛ የግድ አስፈላጊ ላይሆን እንደሚችል ተጠቁሟል።
እነዚህ ቅርንጫፎች በሁሉም የሀገሪቱ ክፍሎች የሚገኙ በመሆናቸው፣ ተገልጋዮች ወደ አዲስ አበባ ሳይመጡ በአቅራቢያቸው አገልግሎት እንዲያገኙ ያስችላቸዋል ተብሏል።
ከፓስፖርት ባለፈም፣ የነዋሪነት ፈቃድና የቪዛ አገልግሎቶች ሙሉ በሙሉ በዲጂታል መንገድ እየተሰጡ ይገኛሉ ብለዋል።
Seledadotio
Seledadotio
3 days ago
ፖለቲከኛ አቶ አበባ አካሉ መታሰራቸው ተሰማ
በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ሰፋ ያለ ትንታኔ በመስጠት እና በፓርቲ ፖለቲካ የሚታወቁት አቶ አበበ በትናንትናው ዕለት መታሰራቸውን የቤተሰብ ምንጮች ለአንዳፍታ ሚዲያ ተናግረዋል፡፡
ፖለቲከኛው በምን ምክንያት እንደታሰሩ ያልታወቀ ሲሆን፤ ባሁኑ ሰአት ሜክሲኮ በሚገኘው የፌዴራል ፖሊስ እንደሚገኙም ቤተሰቦቻቸው ገልጸዋል፡፡
Seledadotio
Seledadotio
በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ሰፋ ያለ ትንታኔ በመስጠት እና በፓርቲ ፖለቲካ የሚታወቁት አቶ አበበ በትናንትናው ዕለት መታሰራቸውን የቤተሰብ ምንጮች ለአንዳፍታ ሚዲያ ተናግረዋል፡፡
ፖለቲከኛው በምን ምክንያት እንደታሰሩ ያልታወቀ ሲሆን፤ ባሁኑ ሰአት ሜክሲኮ በሚገኘው የፌዴራል ፖሊስ እንደሚገኙም ቤተሰቦቻቸው ገልጸዋል፡፡
Seledadotio
Seledadotio
3 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና ዳሰሳ) በኢትዮጵያ እና በአሜሪካ መንግስት መካከል የተፈረመው የ1.616 ቢሊዮን ዶላር የሕዝብ ጤና ትብብር ስምምነት፣ የሀገሪቱን የፖሊሲ ነፃነት፣ ግልፅነት እና እውነተኛ አፈፃፀም አስመልክቶ አዳዲስ ሂሳዊ ጥያቄዎችን ማስነሳቱን አንድ አዲስ ጥናት ይፋ አደረገ። በእንግሊዙ ብሪስቶል ዩኒቨርሲቲ በጤና ኢኮኖሚክስ እና ፖሊሲ ትንተና ባለሙያ የቀረበው ይህ ጥናት፣ ስምምነቱ የሀገሪቱን የጤና ዘርፍ ያጠናክራል ተብሎ ቢነገርለትም፣ ከጎረቤት ሀገራት ተሞክሮ እና ከሀገር ውስጥ ነባራዊ ሁኔታ አኳያ በርካታ የትኩረት ክፍተቶች እንዳሉበት አመልክቷል።
የስምምነቱ ዝርዝር እና የኬንያ ንፅፅር
በታህሳስ 2018 (ዲሴምበር 2025) በጤና ሚኒስትሯ ዶ/ር መቅደስ ዳባ፣ በፋይናንስ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ እና በአሜሪካው አምባሳደር ኤርቪን ማሲንጋ መካከል የተፈረመው ይህ ስምምነት፣ አሜሪካ እስከ 1.166 ቢሊዮን ዶላር (ተጨማሪ የብቃት ድጋፍን ጨምሮ) እና ኢትዮጵያ 450 ሚሊዮን ዶላር በሀገር ውስጥ የሚሸፍኑበት ነው። ነገር ግን ጥናቱ እንደሚያሳየው፣ አጠቃላይ የህዝብ ብዛቷ የኢትዮጵያን ግማሽ ያህል የምትሆነው ጎረቤት ሀገር ኬንያ፣ በተመሳሳይ ጊዜ ከዩናይትድ ስቴትስ ጋር የ2.5 ቢሊዮን ዶላር ስምምነት ተፈራርማለች።
የኢትዮጵያ የህዝብ ብዛት እጅግ የበዛ ሆኖ እያለ፣ ለምን ከኬንያ በእጅጉ ያነሰ የፋይናንስ ድጋፍ ለመቀበል ተስማማች የሚለው ጥያቄ የሙያተኞችን ትኩረት ስቧል። የኢትዮጵያ ተደራዳሪዎች ከህዝብ ብዛታቸው አኳያ ከኬንያ እጥፍ ወይም እስከ 5 ቢሊዮን ዶላር የሚደርስ ድጋፍ ለምን አልጠየቁም የሚለውም ተነስቷል። ከዚህ በተጨማሪም በኬንያ የተደረገው ስምምነት በከፍተኛው ፍርድ ቤት እና በፓርላማ በግልፅነት፣ በህዝብ ተሳትፎ እና በጤና መረጃ ጥበቃ በኩል ተገቢው ምርመራ እንዲደረግበት መታገዱን የሚያስታውሰው ጥናት፣ የኢትዮጵያ ስምምነት በምን ያህል የፓርላማ እና የህግ ባለሙያዎች ምርመራና ይሁንታ አለፈ የሚለውን ይጠይቃል።
የሀገር ውስጥ የመድኃኒት ምርት እና የህዝብ ተቋማት እውነታ
ሌላው በጥናቱ የተነሳው አሳሳቢ ጉዳይ የመድኃኒት አቅርቦት እና የሀገር ውስጥ ምርት እውነታ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ በሐምሌ ወር ለፓርላማ ባደረጉት ንግግር የሀገር ውስጥ የመድኃኒት ምርት አቅም የሀገሪቱን 44 በመቶ ፍላጎት መሸፈን መቻሉን ገልጸው ነበር። ይሁን እንጂ በጥናቱ እንደተመላከተው፣ ይህ ቁጥር በወረቀት ላይ የሚታይ እንጂ በህዝብ የጤና ተቋማት ውስጥ ያለውን የመድኃኒት እጥረት አይገልጽም።
በጥራዝ ነጠቅ መረጃዎች እና በህሙማን ቅሬታዎች እንደታየው፣ የማህበረሰብ አቀፍ የጤና መድህን ክፍያ የሚከፍሉ ወደ 32 ሚሊዮን የሚጠጉ ዜጎች በመንግስት ሆስፒታሎች መድኃኒት በማጣታቸው ምክንያት ከኪሳቸው ተጨማሪ ገንዘብ አውጥተው ከግል ፋርማሲዎች ለመግዛት ይገደዳሉ። ይህም የመንግስት የሀገር ውስጥ ምርት አድጓል የሚለው መረጃ እና በምድር ላይ ያለው እውነታ አለመጣጣሙን ያሳያል።
የመልካም አስተዳደር እና የታማኝነት ጥያቄዎች
ጥናቱ ሲያጠቃልል ደግሞ የጤና ዘርፍ አመራር እና ስኬት መመዘን ያለበት በሚያምሩ ንግግሮች ወይም ስምምነቶች በመፈራረም ሳይሆን በዜጎች ህይወት ላይ በሚያመጣው ተጨባጭ ለውጥ መሆኑን ያሰምርበታል። የጤና ሚኒስቴር ለፓርላማ እና ለጠቅላይ ሚኒስትሩ የሚያቀርባቸው የቁጥር ሪፖርቶች እውነተኝነት በገለልተኛ አካል ሊረጋገጥ እንደሚገባ የተገለጸ ሲሆን፣ የመድኃኒት አቅርቦት እጥረትን ለማስወገድ እና በህዝብ የጤና ተቋማት ላይ እምነትን ለመመለስ ግልፅ አሰራር እና ቁጥጥር ሊኖር እንደሚገባ በጥናቱ አሳስቧል።
የስምምነቱ ዝርዝር እና የኬንያ ንፅፅር
በታህሳስ 2018 (ዲሴምበር 2025) በጤና ሚኒስትሯ ዶ/ር መቅደስ ዳባ፣ በፋይናንስ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ እና በአሜሪካው አምባሳደር ኤርቪን ማሲንጋ መካከል የተፈረመው ይህ ስምምነት፣ አሜሪካ እስከ 1.166 ቢሊዮን ዶላር (ተጨማሪ የብቃት ድጋፍን ጨምሮ) እና ኢትዮጵያ 450 ሚሊዮን ዶላር በሀገር ውስጥ የሚሸፍኑበት ነው። ነገር ግን ጥናቱ እንደሚያሳየው፣ አጠቃላይ የህዝብ ብዛቷ የኢትዮጵያን ግማሽ ያህል የምትሆነው ጎረቤት ሀገር ኬንያ፣ በተመሳሳይ ጊዜ ከዩናይትድ ስቴትስ ጋር የ2.5 ቢሊዮን ዶላር ስምምነት ተፈራርማለች።
የኢትዮጵያ የህዝብ ብዛት እጅግ የበዛ ሆኖ እያለ፣ ለምን ከኬንያ በእጅጉ ያነሰ የፋይናንስ ድጋፍ ለመቀበል ተስማማች የሚለው ጥያቄ የሙያተኞችን ትኩረት ስቧል። የኢትዮጵያ ተደራዳሪዎች ከህዝብ ብዛታቸው አኳያ ከኬንያ እጥፍ ወይም እስከ 5 ቢሊዮን ዶላር የሚደርስ ድጋፍ ለምን አልጠየቁም የሚለውም ተነስቷል። ከዚህ በተጨማሪም በኬንያ የተደረገው ስምምነት በከፍተኛው ፍርድ ቤት እና በፓርላማ በግልፅነት፣ በህዝብ ተሳትፎ እና በጤና መረጃ ጥበቃ በኩል ተገቢው ምርመራ እንዲደረግበት መታገዱን የሚያስታውሰው ጥናት፣ የኢትዮጵያ ስምምነት በምን ያህል የፓርላማ እና የህግ ባለሙያዎች ምርመራና ይሁንታ አለፈ የሚለውን ይጠይቃል።
የሀገር ውስጥ የመድኃኒት ምርት እና የህዝብ ተቋማት እውነታ
ሌላው በጥናቱ የተነሳው አሳሳቢ ጉዳይ የመድኃኒት አቅርቦት እና የሀገር ውስጥ ምርት እውነታ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ በሐምሌ ወር ለፓርላማ ባደረጉት ንግግር የሀገር ውስጥ የመድኃኒት ምርት አቅም የሀገሪቱን 44 በመቶ ፍላጎት መሸፈን መቻሉን ገልጸው ነበር። ይሁን እንጂ በጥናቱ እንደተመላከተው፣ ይህ ቁጥር በወረቀት ላይ የሚታይ እንጂ በህዝብ የጤና ተቋማት ውስጥ ያለውን የመድኃኒት እጥረት አይገልጽም።
በጥራዝ ነጠቅ መረጃዎች እና በህሙማን ቅሬታዎች እንደታየው፣ የማህበረሰብ አቀፍ የጤና መድህን ክፍያ የሚከፍሉ ወደ 32 ሚሊዮን የሚጠጉ ዜጎች በመንግስት ሆስፒታሎች መድኃኒት በማጣታቸው ምክንያት ከኪሳቸው ተጨማሪ ገንዘብ አውጥተው ከግል ፋርማሲዎች ለመግዛት ይገደዳሉ። ይህም የመንግስት የሀገር ውስጥ ምርት አድጓል የሚለው መረጃ እና በምድር ላይ ያለው እውነታ አለመጣጣሙን ያሳያል።
የመልካም አስተዳደር እና የታማኝነት ጥያቄዎች
ጥናቱ ሲያጠቃልል ደግሞ የጤና ዘርፍ አመራር እና ስኬት መመዘን ያለበት በሚያምሩ ንግግሮች ወይም ስምምነቶች በመፈራረም ሳይሆን በዜጎች ህይወት ላይ በሚያመጣው ተጨባጭ ለውጥ መሆኑን ያሰምርበታል። የጤና ሚኒስቴር ለፓርላማ እና ለጠቅላይ ሚኒስትሩ የሚያቀርባቸው የቁጥር ሪፖርቶች እውነተኝነት በገለልተኛ አካል ሊረጋገጥ እንደሚገባ የተገለጸ ሲሆን፣ የመድኃኒት አቅርቦት እጥረትን ለማስወገድ እና በህዝብ የጤና ተቋማት ላይ እምነትን ለመመለስ ግልፅ አሰራር እና ቁጥጥር ሊኖር እንደሚገባ በጥናቱ አሳስቧል።
4 days ago
የሴዶ እና የጆኒ ታላቅ የMMA ፍልሚያ ነሐሴ 21 ይካሄዳል!
#fastmereja :-በኢትዮጵያ የማርሻል አርትስ እና የቦክስ ስፖርት ታሪክ ያልተነካውን እምቅ አቅም ለዓለም ለማሳየትና ስፖርቱን ለወጣቶች የቋሚ ገቢ ምንጭ ለማድረግ ያለመው ''አድዋ ፋይት ናይት 2" (ETFC 002) ታላቅ የውድድር ምሽት ነሀሴ 21 እንደሚካሄድ በዛሬዉ እለት ተገለፀ።
ነሀሴ 21 በሚካሄደው በዚህ ውድድር ላይ በስፖርት አፍቃሪያን ዘንድ ከፍተኛ ትኩረትን የሳበው እና በጉጉት የሚጠበቀው ዋና ፍልሚያ (Main Event) በጆኒ (Johnny) እና በሴዶ (Sedo) መካከል የሚደረገው ድብልቅ ማርሻል አርት (MMA) ግጥሚያ እንደሆነ ተገልጿል።
ዛሬ በተሰጠው የጋዜጣዊ መግለጫ ወቅት ተወዳዳሪዎች በፊት ለፊት ፍጥጫ (Face-to face) የተገናኙ ሲሆን እርስ በእርስ ያቀረቧቸው የተፎካካሪነት እና የስነ-ልቦና የበላይነት የመውሰጃ አስተያየቶች በስፍራው የነበረውን ስሜት ያጋገሉት ሲሆን፣ ሁለቱም ስፖርተኞች ለነሐሴ 21ዱ ታላቅ ፍልሚያ ያላቸውን ከፍተኛ ዝግጁነትና የማሸነፍ በራስ መተማመን አሳይተዋል።
የውድድሩ አዘጋጅና የስዊት ቦክስ መስራች እና ስራ አ አቶ ጌታቸው መለሰ በበኩላቸው፣ ETFC 002 የቀደመው ETFC 001 ከተካሄደበት ፍጥነትና ሁኔታ በተሻለ መልኩ በከፍተኛ ደረጃ ተዘጋጅቶ የቀረበ መሆኑን ገልጸዋል።
አዘጋጆቹ ለፕሮግራሙ መዘገየት ይቅርታ በመጠየቅ፣በተወዳዳሪዎቹ የስነ-ምግባር ጥንካሬ ላይ ሙሉ እምነት እንዳላቸውና ስፖርተኞቹ ሀገራቸውን በዓለም አቀፍ መድረክ ማስጠራት የሚችሉ መሆናቸውን አብራርተዋል።
በምሽቱ 11 የተመረጡ ፍልሚያዎች የሚካሄዱ ሲሆን፣ 4 የቦክስ (Boxing) 4 የኤምኤምኤ (MMA) 3 የሙአይ ታይ (Muay Thai) ፍልሚያዎች ናቸው።
በዝግጅቱ ላይ የሴቶች ተሳትፎ ልዩ ቦታ የተሰጠው ሲሆን፣ አትሌት አብስላት እና ዛራ በተወዳዳሪነት የሚሳተፉ ሲሆን በቀጣዩ «አድዋ ፋይት ናይት 003» ውድድር ላይ ደግሞ የሴት ተወዳዳሪዎች ቁጥር እንዲጨምርና ሰፊ ተሳትፎ እንዲኖራቸው ትኩረት ተሰጥቶ እንደሚሰራ ተጠቅሷል።
በሌላ በኩል፣ በቀደሙት ዝግጅቶች የነበረውን የመቀመጫ መደራረብ ችግር ሙሉ በሙሉ ለመቅረፍ የተሰራ ሲሆን በዚህም ተመልካቾች ትኬት በሚቆርጡበት ወቅት ቀጥታ የመቀመጫ ቦታቸውን (Seat) መርጠው እንዲይዙ እንደሚደረግም ነዉ የተገለፀዉ።
አዘጋጆቹ እንዳብራሩት፣ በቅርቡ በሚካሄዱት ETFC-003 እና ETFC-004 የውድድር መድረኮች ላይ የሀገር ውስጥ ስፖርተኞች ከውጭ ሀገር ተወዳዳሪዎች ጋር እንዲጋጠሙ እንደሚደረግ የተገለፀ ሲሆን ይህም በሚቀጥሉት ሁለት ዓመታት ውስጥ እንደ ኡሲክ (Usyk) ያሉ ታዋቂ የዓለም አቀፍ ቦክስ ውድድሮችን በኢትዮጵያ ውስጥ ለማዘጋጀት ለተያዘው ታላቅ ዕቅድ መንገድ የሚከፍት ነው ተብሏል።
ይህ ዝግጅት በአድዋ ድል መታሰቢያ፣ በአዲስ አበባ ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ፣ የስፖርት አመራሮች እንዲሁም አጋር ድርጅቶች አስተዋጽኦ የሚካሄድ ሲሆን፣ የስፖርት አፍቃሪያን የነሐሴ 21ዱን የሴዶ እና ጆኒ ፍልሚያ በከፍተኛ ጉጉት በመጠበቅ ላይ ይገኛሉ።
📷 ከበደ መክብብ
#fastmereja :-በኢትዮጵያ የማርሻል አርትስ እና የቦክስ ስፖርት ታሪክ ያልተነካውን እምቅ አቅም ለዓለም ለማሳየትና ስፖርቱን ለወጣቶች የቋሚ ገቢ ምንጭ ለማድረግ ያለመው ''አድዋ ፋይት ናይት 2" (ETFC 002) ታላቅ የውድድር ምሽት ነሀሴ 21 እንደሚካሄድ በዛሬዉ እለት ተገለፀ።
ነሀሴ 21 በሚካሄደው በዚህ ውድድር ላይ በስፖርት አፍቃሪያን ዘንድ ከፍተኛ ትኩረትን የሳበው እና በጉጉት የሚጠበቀው ዋና ፍልሚያ (Main Event) በጆኒ (Johnny) እና በሴዶ (Sedo) መካከል የሚደረገው ድብልቅ ማርሻል አርት (MMA) ግጥሚያ እንደሆነ ተገልጿል።
ዛሬ በተሰጠው የጋዜጣዊ መግለጫ ወቅት ተወዳዳሪዎች በፊት ለፊት ፍጥጫ (Face-to face) የተገናኙ ሲሆን እርስ በእርስ ያቀረቧቸው የተፎካካሪነት እና የስነ-ልቦና የበላይነት የመውሰጃ አስተያየቶች በስፍራው የነበረውን ስሜት ያጋገሉት ሲሆን፣ ሁለቱም ስፖርተኞች ለነሐሴ 21ዱ ታላቅ ፍልሚያ ያላቸውን ከፍተኛ ዝግጁነትና የማሸነፍ በራስ መተማመን አሳይተዋል።
የውድድሩ አዘጋጅና የስዊት ቦክስ መስራች እና ስራ አ አቶ ጌታቸው መለሰ በበኩላቸው፣ ETFC 002 የቀደመው ETFC 001 ከተካሄደበት ፍጥነትና ሁኔታ በተሻለ መልኩ በከፍተኛ ደረጃ ተዘጋጅቶ የቀረበ መሆኑን ገልጸዋል።
አዘጋጆቹ ለፕሮግራሙ መዘገየት ይቅርታ በመጠየቅ፣በተወዳዳሪዎቹ የስነ-ምግባር ጥንካሬ ላይ ሙሉ እምነት እንዳላቸውና ስፖርተኞቹ ሀገራቸውን በዓለም አቀፍ መድረክ ማስጠራት የሚችሉ መሆናቸውን አብራርተዋል።
በምሽቱ 11 የተመረጡ ፍልሚያዎች የሚካሄዱ ሲሆን፣ 4 የቦክስ (Boxing) 4 የኤምኤምኤ (MMA) 3 የሙአይ ታይ (Muay Thai) ፍልሚያዎች ናቸው።
በዝግጅቱ ላይ የሴቶች ተሳትፎ ልዩ ቦታ የተሰጠው ሲሆን፣ አትሌት አብስላት እና ዛራ በተወዳዳሪነት የሚሳተፉ ሲሆን በቀጣዩ «አድዋ ፋይት ናይት 003» ውድድር ላይ ደግሞ የሴት ተወዳዳሪዎች ቁጥር እንዲጨምርና ሰፊ ተሳትፎ እንዲኖራቸው ትኩረት ተሰጥቶ እንደሚሰራ ተጠቅሷል።
በሌላ በኩል፣ በቀደሙት ዝግጅቶች የነበረውን የመቀመጫ መደራረብ ችግር ሙሉ በሙሉ ለመቅረፍ የተሰራ ሲሆን በዚህም ተመልካቾች ትኬት በሚቆርጡበት ወቅት ቀጥታ የመቀመጫ ቦታቸውን (Seat) መርጠው እንዲይዙ እንደሚደረግም ነዉ የተገለፀዉ።
አዘጋጆቹ እንዳብራሩት፣ በቅርቡ በሚካሄዱት ETFC-003 እና ETFC-004 የውድድር መድረኮች ላይ የሀገር ውስጥ ስፖርተኞች ከውጭ ሀገር ተወዳዳሪዎች ጋር እንዲጋጠሙ እንደሚደረግ የተገለፀ ሲሆን ይህም በሚቀጥሉት ሁለት ዓመታት ውስጥ እንደ ኡሲክ (Usyk) ያሉ ታዋቂ የዓለም አቀፍ ቦክስ ውድድሮችን በኢትዮጵያ ውስጥ ለማዘጋጀት ለተያዘው ታላቅ ዕቅድ መንገድ የሚከፍት ነው ተብሏል።
ይህ ዝግጅት በአድዋ ድል መታሰቢያ፣ በአዲስ አበባ ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ፣ የስፖርት አመራሮች እንዲሁም አጋር ድርጅቶች አስተዋጽኦ የሚካሄድ ሲሆን፣ የስፖርት አፍቃሪያን የነሐሴ 21ዱን የሴዶ እና ጆኒ ፍልሚያ በከፍተኛ ጉጉት በመጠበቅ ላይ ይገኛሉ።
📷 ከበደ መክብብ
4 days ago
በጻድቃኔ ደብረ ምጥማቅ ቅድስት ማርያም ገዳም በተከሰተ የመሬት መንሸራተት አደጋ የ14 ሰዎች ሕይወት አለፈ!
በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን በሚገኘው በጻድቃኔ ደብረ ምጥማቅ ቅድስት ማርያም ገዳም ድንገት በተከሰተ የርዕደ መሬትና የመሬት መንሸራተት አደጋ የ14 ምዕመናን ሕይወት ማለፉንና በሰባት ሰዎች ላይ የአካል ጉዳት መድረሱን የዞኑ አስተዳደር መምሪያ አስታወቀ።
በአደጋው በ5 ሰዎች ላይ ከፍተኛ እና በ2 ሰዎች ላይ ደግሞ መለስተኛ የአካል ጉዳት መድረሱን የሰሜን ሸዋ ዞን አስተዳደር መምሪያ ገልጿል።
መምሪያው በአደጋው ህይወታቸውን ባጡ እና ጉዳት በደረሰባቸው ወገኖች የተሰማውን መሪር ኀዘን የገለጸ ሲሆን፣ አደጋው ከተከሰተ በኋላ በስፍራው በመገኘት የተቀናጀ የነፍስ አድኖና የሕክምና እርዳታ ድጋፍ ላደረጉት የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ የማነብርሀን ተስፋ፣ የአመራር አካላት፣ ለፀጥታ ኃይሎች፣ ለሕክምና ባለሙያዎችና ለአካባቢው ማኅበረሰብ ከፍተኛ ምስጋና አቅርቧል።
በተጨማሪም በአደጋው ስፍራ በመገኘት ለሞቱት ጸሎተ ፍትሐት፣ ለተጎዱት ጸሎትና ለተከፉ ወገኖች የማጽናኛ ትምህርተ ወንጌልና አባታዊ ቃለ በረከት እየሰጡ ለሚገኙት ለብፁዕ ሊቀ ጳጳስ አቡነ ቀሌምንጦስ ያለውን አክብሮት ገልጻል።
Seledadotio
Seledadotio
በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን በሚገኘው በጻድቃኔ ደብረ ምጥማቅ ቅድስት ማርያም ገዳም ድንገት በተከሰተ የርዕደ መሬትና የመሬት መንሸራተት አደጋ የ14 ምዕመናን ሕይወት ማለፉንና በሰባት ሰዎች ላይ የአካል ጉዳት መድረሱን የዞኑ አስተዳደር መምሪያ አስታወቀ።
በአደጋው በ5 ሰዎች ላይ ከፍተኛ እና በ2 ሰዎች ላይ ደግሞ መለስተኛ የአካል ጉዳት መድረሱን የሰሜን ሸዋ ዞን አስተዳደር መምሪያ ገልጿል።
መምሪያው በአደጋው ህይወታቸውን ባጡ እና ጉዳት በደረሰባቸው ወገኖች የተሰማውን መሪር ኀዘን የገለጸ ሲሆን፣ አደጋው ከተከሰተ በኋላ በስፍራው በመገኘት የተቀናጀ የነፍስ አድኖና የሕክምና እርዳታ ድጋፍ ላደረጉት የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ የማነብርሀን ተስፋ፣ የአመራር አካላት፣ ለፀጥታ ኃይሎች፣ ለሕክምና ባለሙያዎችና ለአካባቢው ማኅበረሰብ ከፍተኛ ምስጋና አቅርቧል።
በተጨማሪም በአደጋው ስፍራ በመገኘት ለሞቱት ጸሎተ ፍትሐት፣ ለተጎዱት ጸሎትና ለተከፉ ወገኖች የማጽናኛ ትምህርተ ወንጌልና አባታዊ ቃለ በረከት እየሰጡ ለሚገኙት ለብፁዕ ሊቀ ጳጳስ አቡነ ቀሌምንጦስ ያለውን አክብሮት ገልጻል።
Seledadotio
Seledadotio
4 days ago
የቢሾፍቱው ግዙፍ ኤርፖርት የገንዘብ ድጋፍ ማጽደቅ ስምንት ወራት ይፈጃል ተባለ
የኢትዮጵያ አየር መንገድ በቢሾፍቱ ለሚገነባው አዲስ ሜጋ ኤርፖርት የሚያስፈልገውን የቢሊዮን ዶላር ብድር የማጽደቅ ሂደት ስምንት ወራት እንደሚፈጅና እስከ መጋቢት 2019 ዓ.ም ድረስ እንደሚጠናቀቅ አስታወቀ።
አየር መንገዱ የመሬት መንጥር እና የተፈናቀሉ አርሶ አደሮችን መልሶ የማቋቋም ስራዎች በከፍተኛ ሁኔታ መጠናቀቃቸውን ገልጿል።
ዋና ስራ አስፈጻሚው አቶ መስፍን ጣሰው እንደተናገሩት፣ የግንባታ ተቋራጮች ተጨማሪ ጊዜ በመጠየቃቸው የኮንትራክተሮች መረጣ ማጠናቀቂያ ጊዜ ከነሐሴ ወር ወደ መጪው ጥር መራዘሙን አስረድተዋል።
Via capital
የኢትዮጵያ አየር መንገድ በቢሾፍቱ ለሚገነባው አዲስ ሜጋ ኤርፖርት የሚያስፈልገውን የቢሊዮን ዶላር ብድር የማጽደቅ ሂደት ስምንት ወራት እንደሚፈጅና እስከ መጋቢት 2019 ዓ.ም ድረስ እንደሚጠናቀቅ አስታወቀ።
አየር መንገዱ የመሬት መንጥር እና የተፈናቀሉ አርሶ አደሮችን መልሶ የማቋቋም ስራዎች በከፍተኛ ሁኔታ መጠናቀቃቸውን ገልጿል።
ዋና ስራ አስፈጻሚው አቶ መስፍን ጣሰው እንደተናገሩት፣ የግንባታ ተቋራጮች ተጨማሪ ጊዜ በመጠየቃቸው የኮንትራክተሮች መረጣ ማጠናቀቂያ ጊዜ ከነሐሴ ወር ወደ መጪው ጥር መራዘሙን አስረድተዋል።
Via capital
Sponsored by
Surafel
4 days ago
ኩባንያችን 8ኛውን ዙር የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር በይፋ አስጀመረ!
ኩባንያችን የአረንጓዴ ኦፕሬተርነት ጉዞውን በማጠናከር፣ ዛሬ በሀገር አቀፍ ደረጃ “ለአረንጓዴ ኢትዮጵያ” በሚል መሪ ቃል 250 ሺህ ችግኞችን በስኬት ተክሏል፡፡ በዚህም በአዲስ አበባ እንጦጦ (ቁስቋም ማዞሪያ) እንዲሁም በመላው ሀገሪቱ በሚገኙ ከተሞች አረንጓዴ አሻራችንን አሳርፈናል፡፡
በመርሃ-ግብሩ ላይ ዋና ሥራ አስፈጻሚያችን ፍሬሕይወት ታምሩ እንደገለጹት፤ ይህ ተግባር ኩባንያችን በዘላቂነት ስትራቴጂው (Sustainability Strategy) የሚያከናውናቸው ተግባራት አካል ሲሆን፣ ባለፉት ሰባት ዓመታት ከተተከሉ ከ4.6 ሚሊዮን በላይ ችግኞች 82.7% እንዲጸድቁ መደረጉን አብራርተዋል።
በተጨማሪም በታዳሽ የኃይል ኢንቨስትመንቶች፣ በፀሐይ ኃይል የሚሠሩ የኔትወርክ መሠረተ-ልማቶች እና ኃይል ቆጣቢ አረንጓዴ የዳታ ማዕከላት አማካኝነት የካርቦን ልቀት ቅነሳን ማሳካት ተችሏል። በተመሳሳይ በገነባናቸው ከ9 በላይ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ መሙያ ጣቢያዎች ከ481 ሺህ በላይ ተሽከርካሪዎችን በማስተናገድ፣ ከ15.4 ሚሊዮን ኪሎግራም በላይ የካርቦን ልቀትን መከላከል ተችሏል፤ ይህም ከ76 ሺህ በላይ ዛፎችን ከመትከል ጋር እኩል ፋይዳ አለው።
የጉለሌ ክፍለ ከተማ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ወልዴ ወገሴ በመርሃ-ግብሩ ባስተላለፉት መልዕክት፤ ኢትዮ ቴሌኮም ችግኝ መትከል ብቻ ሳይሆን ለመንከባከብ ትኩረት የሚሰጥ ተቋም መሆኑን ገልጸው፣ ከዚህ ቀደም የተተከሉ ችግኞች ወደ ጫካነት መቀየራቸውን በመጥቀስ ልባዊ ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡
በ8ኛው ዙር መርሃ-ግብር ለተከላና እንክብካቤ ሥራዎች ከ2,000 በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የሥራ ዕድል የሚፈጠር ሲሆን፣ ባለፉት ሰባት ዓመታት ውስጥ በአጠቃላይ ከ24.8 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠር ተችሏል፡፡
በዚህ የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር ላይ በንቃት ለተሳተፋችሁ የኩባንያችን ቤተሰቦች፣ አጋሮቻችን እና የመትከያ ቦታ ላመቻቻችሁ የመንግስት አካላት ምስጋና እናቀርባለን፡፡
ለበለጠ፡ https://bit.ly/4xhlXxF
#digitalethiopia #digitalafrica #gsma #itu #worldbank #oecd #g6countries
ኩባንያችን የአረንጓዴ ኦፕሬተርነት ጉዞውን በማጠናከር፣ ዛሬ በሀገር አቀፍ ደረጃ “ለአረንጓዴ ኢትዮጵያ” በሚል መሪ ቃል 250 ሺህ ችግኞችን በስኬት ተክሏል፡፡ በዚህም በአዲስ አበባ እንጦጦ (ቁስቋም ማዞሪያ) እንዲሁም በመላው ሀገሪቱ በሚገኙ ከተሞች አረንጓዴ አሻራችንን አሳርፈናል፡፡
በመርሃ-ግብሩ ላይ ዋና ሥራ አስፈጻሚያችን ፍሬሕይወት ታምሩ እንደገለጹት፤ ይህ ተግባር ኩባንያችን በዘላቂነት ስትራቴጂው (Sustainability Strategy) የሚያከናውናቸው ተግባራት አካል ሲሆን፣ ባለፉት ሰባት ዓመታት ከተተከሉ ከ4.6 ሚሊዮን በላይ ችግኞች 82.7% እንዲጸድቁ መደረጉን አብራርተዋል።
በተጨማሪም በታዳሽ የኃይል ኢንቨስትመንቶች፣ በፀሐይ ኃይል የሚሠሩ የኔትወርክ መሠረተ-ልማቶች እና ኃይል ቆጣቢ አረንጓዴ የዳታ ማዕከላት አማካኝነት የካርቦን ልቀት ቅነሳን ማሳካት ተችሏል። በተመሳሳይ በገነባናቸው ከ9 በላይ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ መሙያ ጣቢያዎች ከ481 ሺህ በላይ ተሽከርካሪዎችን በማስተናገድ፣ ከ15.4 ሚሊዮን ኪሎግራም በላይ የካርቦን ልቀትን መከላከል ተችሏል፤ ይህም ከ76 ሺህ በላይ ዛፎችን ከመትከል ጋር እኩል ፋይዳ አለው።
የጉለሌ ክፍለ ከተማ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ወልዴ ወገሴ በመርሃ-ግብሩ ባስተላለፉት መልዕክት፤ ኢትዮ ቴሌኮም ችግኝ መትከል ብቻ ሳይሆን ለመንከባከብ ትኩረት የሚሰጥ ተቋም መሆኑን ገልጸው፣ ከዚህ ቀደም የተተከሉ ችግኞች ወደ ጫካነት መቀየራቸውን በመጥቀስ ልባዊ ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡
በ8ኛው ዙር መርሃ-ግብር ለተከላና እንክብካቤ ሥራዎች ከ2,000 በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የሥራ ዕድል የሚፈጠር ሲሆን፣ ባለፉት ሰባት ዓመታት ውስጥ በአጠቃላይ ከ24.8 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠር ተችሏል፡፡
በዚህ የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር ላይ በንቃት ለተሳተፋችሁ የኩባንያችን ቤተሰቦች፣ አጋሮቻችን እና የመትከያ ቦታ ላመቻቻችሁ የመንግስት አካላት ምስጋና እናቀርባለን፡፡
ለበለጠ፡ https://bit.ly/4xhlXxF
#digitalethiopia #digitalafrica #gsma #itu #worldbank #oecd #g6countries
4 days ago
ኩባንያችን 8ኛውን ዙር የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር በይፋ አስጀመረ!
ኩባንያችን የአረንጓዴ ኦፕሬተርነት ጉዞውን በማጠናከር፣ ዛሬ በሀገር አቀፍ ደረጃ “ለአረንጓዴ ኢትዮጵያ” በሚል መሪ ቃል 250 ሺህ ችግኞችን በስኬት ተክሏል፡፡ በዚህም በአዲስ አበባ እንጦጦ (ቁስቋም ማዞሪያ) እንዲሁም በመላው ሀገሪቱ በሚገኙ ከተሞች አረንጓዴ አሻራችንን አሳርፈናል፡፡
በመርሃ-ግብሩ ላይ ዋና ሥራ አስፈጻሚያችን ፍሬሕይወት ታምሩ እንደገለጹት፤ ይህ ተግባር ኩባንያችን በዘላቂነት ስትራቴጂው (Sustainability Strategy) የሚያከናውናቸው ተግባራት አካል ሲሆን፣ ባለፉት ሰባት ዓመታት ከተተከሉ ከ4.6 ሚሊዮን በላይ ችግኞች 82.7% እንዲጸድቁ መደረጉን አብራርተዋል።
በተጨማሪም በታዳሽ የኃይል ኢንቨስትመንቶች፣ በፀሐይ ኃይል የሚሠሩ የኔትወርክ መሠረተ-ልማቶች እና ኃይል ቆጣቢ አረንጓዴ የዳታ ማዕከላት አማካኝነት የካርቦን ልቀት ቅነሳን ማሳካት ተችሏል። በተመሳሳይ በገነባናቸው ከ9 በላይ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ መሙያ ጣቢያዎች ከ481 ሺህ በላይ ተሽከርካሪዎችን በማስተናገድ፣ ከ15.4 ሚሊዮን ኪሎግራም በላይ የካርቦን ልቀትን መከላከል ተችሏል፤ ይህም ከ76 ሺህ በላይ ዛፎችን ከመትከል ጋር እኩል ፋይዳ አለው።
የጉለሌ ክፍለ ከተማ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ወልዴ ወገሴ በመርሃ-ግብሩ ባስተላለፉት መልዕክት፤ ኢትዮ ቴሌኮም ችግኝ መትከል ብቻ ሳይሆን ለመንከባከብ ትኩረት የሚሰጥ ተቋም መሆኑን ገልጸው፣ ከዚህ ቀደም የተተከሉ ችግኞች ወደ ጫካነት መቀየራቸውን በመጥቀስ ልባዊ ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡
በ8ኛው ዙር መርሃ-ግብር ለተከላና እንክብካቤ ሥራዎች ከ2,000 በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የሥራ ዕድል የሚፈጠር ሲሆን፣ ባለፉት ሰባት ዓመታት ውስጥ በአጠቃላይ ከ24.8 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠር ተችሏል፡፡
በዚህ የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር ላይ በንቃት ለተሳተፋችሁ የኩባንያችን ቤተሰቦች፣ አጋሮቻችን እና የመትከያ ቦታ ላመቻቻችሁ የመንግስት አካላት ምስጋና እናቀርባለን፡፡
ለበለጠ፡ https://bit.ly/4xhlXxF
#digitalethiopia #digitalafrica #gsma #itu #worldbank #oecd #g6countries
ኩባንያችን የአረንጓዴ ኦፕሬተርነት ጉዞውን በማጠናከር፣ ዛሬ በሀገር አቀፍ ደረጃ “ለአረንጓዴ ኢትዮጵያ” በሚል መሪ ቃል 250 ሺህ ችግኞችን በስኬት ተክሏል፡፡ በዚህም በአዲስ አበባ እንጦጦ (ቁስቋም ማዞሪያ) እንዲሁም በመላው ሀገሪቱ በሚገኙ ከተሞች አረንጓዴ አሻራችንን አሳርፈናል፡፡
በመርሃ-ግብሩ ላይ ዋና ሥራ አስፈጻሚያችን ፍሬሕይወት ታምሩ እንደገለጹት፤ ይህ ተግባር ኩባንያችን በዘላቂነት ስትራቴጂው (Sustainability Strategy) የሚያከናውናቸው ተግባራት አካል ሲሆን፣ ባለፉት ሰባት ዓመታት ከተተከሉ ከ4.6 ሚሊዮን በላይ ችግኞች 82.7% እንዲጸድቁ መደረጉን አብራርተዋል።
በተጨማሪም በታዳሽ የኃይል ኢንቨስትመንቶች፣ በፀሐይ ኃይል የሚሠሩ የኔትወርክ መሠረተ-ልማቶች እና ኃይል ቆጣቢ አረንጓዴ የዳታ ማዕከላት አማካኝነት የካርቦን ልቀት ቅነሳን ማሳካት ተችሏል። በተመሳሳይ በገነባናቸው ከ9 በላይ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ መሙያ ጣቢያዎች ከ481 ሺህ በላይ ተሽከርካሪዎችን በማስተናገድ፣ ከ15.4 ሚሊዮን ኪሎግራም በላይ የካርቦን ልቀትን መከላከል ተችሏል፤ ይህም ከ76 ሺህ በላይ ዛፎችን ከመትከል ጋር እኩል ፋይዳ አለው።
የጉለሌ ክፍለ ከተማ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ወልዴ ወገሴ በመርሃ-ግብሩ ባስተላለፉት መልዕክት፤ ኢትዮ ቴሌኮም ችግኝ መትከል ብቻ ሳይሆን ለመንከባከብ ትኩረት የሚሰጥ ተቋም መሆኑን ገልጸው፣ ከዚህ ቀደም የተተከሉ ችግኞች ወደ ጫካነት መቀየራቸውን በመጥቀስ ልባዊ ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡
በ8ኛው ዙር መርሃ-ግብር ለተከላና እንክብካቤ ሥራዎች ከ2,000 በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የሥራ ዕድል የሚፈጠር ሲሆን፣ ባለፉት ሰባት ዓመታት ውስጥ በአጠቃላይ ከ24.8 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠር ተችሏል፡፡
በዚህ የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር ላይ በንቃት ለተሳተፋችሁ የኩባንያችን ቤተሰቦች፣ አጋሮቻችን እና የመትከያ ቦታ ላመቻቻችሁ የመንግስት አካላት ምስጋና እናቀርባለን፡፡
ለበለጠ፡ https://bit.ly/4xhlXxF
#digitalethiopia #digitalafrica #gsma #itu #worldbank #oecd #g6countries
4 days ago
ከሞጃና ወደራ ወረዳ አስተዳደር ምክርቤት የተሰጠ የሀዘን መግለጫ
በታላቋ ገዳም በጻድቃኔ ደብረ ምጥማቅ ቅድስት ማርያም ገዳም ድንገት በተከሰተ ርዕደ መሬትና የመሬት መንሸራተት አደጋ የ14 ሰው ሕይወት አለፈ።
በመሬት መንሸራተቱ የ14 ምዕመናን ሂወት ሲያልፍ በ5 ሰው ላይ ከፍተኛ ጉዳት የደረሰ ሲሆን በ2 ሰዎች ላይ መለስተኛ ጉዳት በመድረሱ የወረዳዉ አስተዳደር ምክርቤት መሪር ኀዘኑን ገልፆል ።
የወረዳዉ ዋና አስተዳዳሪ አቶ የማነብርሀን ተስፈ ጨምሮ የወረዳ አስተባባሪ አመራርና የፀጥታ አመራሩ እቦታዉ ላይ በመገኘት ነፍስ በማዳን እርብርቡ ላይ ሁለተናዊ ድጋፍ አድርገዋል።
የህክምና ባለሙያዎች የአካባቢዉ ማህበረሰብ በቦታዉ ላይ በመገኘት የተጎዱ ወገኖችን የመጀመሪያ ህክምና እርዳታ እንዲያገኙ ብርቱ ትግል አድርገዋል።
ብፁዕ ሊቀ ጳጳስ አቡነ ቀሌምንጦስ በስፍራው የተገኙ ሲሆን ለሞቱ ወገኖቻችን ጸሎተ ፍትሐት ለተጎዱት ጸሎት ላዘኑ ወገኖቻችን የማጽናኛ ትምህርተ ወንጌልና አባታዊ ቃለ በረከት በመስጠት ላይ ይገኛሉ ።
በታላቋ ገዳም በጻድቃኔ ደብረ ምጥማቅ ቅድስት ማርያም ገዳም ድንገት በተከሰተ ርዕደ መሬትና የመሬት መንሸራተት አደጋ የ14 ሰው ሕይወት አለፈ።
በመሬት መንሸራተቱ የ14 ምዕመናን ሂወት ሲያልፍ በ5 ሰው ላይ ከፍተኛ ጉዳት የደረሰ ሲሆን በ2 ሰዎች ላይ መለስተኛ ጉዳት በመድረሱ የወረዳዉ አስተዳደር ምክርቤት መሪር ኀዘኑን ገልፆል ።
የወረዳዉ ዋና አስተዳዳሪ አቶ የማነብርሀን ተስፈ ጨምሮ የወረዳ አስተባባሪ አመራርና የፀጥታ አመራሩ እቦታዉ ላይ በመገኘት ነፍስ በማዳን እርብርቡ ላይ ሁለተናዊ ድጋፍ አድርገዋል።
የህክምና ባለሙያዎች የአካባቢዉ ማህበረሰብ በቦታዉ ላይ በመገኘት የተጎዱ ወገኖችን የመጀመሪያ ህክምና እርዳታ እንዲያገኙ ብርቱ ትግል አድርገዋል።
ብፁዕ ሊቀ ጳጳስ አቡነ ቀሌምንጦስ በስፍራው የተገኙ ሲሆን ለሞቱ ወገኖቻችን ጸሎተ ፍትሐት ለተጎዱት ጸሎት ላዘኑ ወገኖቻችን የማጽናኛ ትምህርተ ወንጌልና አባታዊ ቃለ በረከት በመስጠት ላይ ይገኛሉ ።
Comments