15 hours ago
ቱሪዝም - የኢትዮጵያን ብልጽግና ማረጋገጫ አንዱ መሳሪያ
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 28፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ኢትዮጵያ ውስጥ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ የቱሪዝም ዘርፉ ከዋና ዋናዎቹ የክፍለ ኢኮኖሚው ምሰሶዎች ዝርዝር በመግባቱ ለዘርፉ በርካታ መሰረተ ልማቶች ተሰርተዋል፡፡
ኢትዮጵያም ለሌሎችም የሚተርፍ ገቢን መፍጠር የሚያስችል እምቅ የቱሪዝም ሃብት ቢኖራትም እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ በሚገባው ልክ አልተጠቀመችበትም ነበር።
ዘርፉ እንዲያንሰራራ ፖሊሲ የማውጣት፣ ተቋማትን የማዋቀር፣ አዳዲስ ልማቶችን የማከናወን ሥራ ተከናውኗል፡፡
ከለውጡ ወዲህ በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች የሚገኙ ቅርሶችን ከመጠገን ባለፈ አዳዲስ የቱሪዝም መዳረሻዎች ተገንብተዋል፡፡
የኢትዮጵያ የቱሪዝም ዘርፍ ከፍተኛ እመርታ በማሳየት የሀገሪቱ ዋና የኢኮኖሚ ምንጭ እየሆነ መጥቷል።
የመደመር እሳቤ የኢትዮጵያን የቱሪዝም ዘርፍ ከነበረበት መዘናጋት በማውጣት የሀገሪቱን ብልጽግና ከሚያረጋግጡ ዋና ዋና የኢኮኖሚ ምሰሶዎች አንዱ እንዲሆን አድርጎታል፡፡
መንግሥት ዘርፉን እንደ አንድ ስትራቴጂካዊ የኢኮኖሚ ምሰሶ አድርጎ በመቅረጽ፣ አዳዲስ ግዙፍ መዳረሻዎችን በመገንባት እና ነባር የባህል፣ የታሪክና የተፈጥሮ ጸጋዎችን በማዘመን ረገድ ከፍተኛ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ይገኛል።
ቱሪዝምን ከተፈጥሮ ጥበቃ እና ከማህበረሰብ ልማት ጋር ያቀናጁ የገበታ ለሸገር፣ ገበታ ለሀገር እና ገበታ ለትውልድ ሜጋ ፕሮጀክቶችን መቅረጽና መተግበር ነው።
በርካታ የሀገር ውስጥ እና የውጭ ሀገር ጎብኚዎችን በመሳብ ለሀገሪቱ ገቢና የስራ ዕድል ፈጠራ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል፡፡
ለዘርፉ እድገት መንግሥት በሰጠው ትኩረት አዳዲስ መዳረሻዎችና መሠረተ ልማቶች ተገንብተዋል፡፡
በአዲስ አበባ ከተማ እና በሌሎችም የሀገሪቱ ከተሞች የተከናወኑት የኮሪደር ልማቶች የከተሞችን ውበት በማጎልበት ምቹ ሁኔታን በመፍጠር ቱሪዝሙን ማነቃቃት ተችሏል፡፡
የላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናት፣ የፋሲለደስ ግንብ እና የጁገል ግንብ የመሳሰሉ አንጋፋ ቅርሶችን የመጠበቅና የዕድሳት ሥራዎች በስፋት ተግባራዊ ተደርገዋል፡፡
ከውጭ ጎብኚዎች ባለፈ፣ የሀገር ውስጥ ቱሪዝም ከፍተኛ እድገት እያሳየ ሲሆን፤ ዜጎች ሀገራቸውን እንዲያውቁና እንዲጎበኙ በማድረግ፤ የህዝብ ለህዝብ ትስስርን አጠናክሯል።
የኢትዮጵያ የቱሪዝም ዘርፍ እመርታ የሀገሪቱን አወንታዊ ገጽታ በዓለም አቀፍ ደረጃ በማስተዋወቅ ረገድ የማይተካ ሚና አለው።
የቱሪዝም መዳረሻዎችን በዘመናዊ መንገድ የማልማትና አገልግሎቶችን የማዘመን ሥራዎችም በስፋት እየተሰሩ ነው፡፡
ኢኮኖሚው በብዝሃ ዘርፍ ላይ እንዲመሰረት መደረጉ በቱሪዝም ዘርፍ ያለውን እምቅ አቅም ይበልጥ መጠቀም የሚያስችል ዕድል ፈጥሯል።
በወንድማገኝ ጸጋዬ
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 28፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ኢትዮጵያ ውስጥ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ የቱሪዝም ዘርፉ ከዋና ዋናዎቹ የክፍለ ኢኮኖሚው ምሰሶዎች ዝርዝር በመግባቱ ለዘርፉ በርካታ መሰረተ ልማቶች ተሰርተዋል፡፡
ኢትዮጵያም ለሌሎችም የሚተርፍ ገቢን መፍጠር የሚያስችል እምቅ የቱሪዝም ሃብት ቢኖራትም እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ በሚገባው ልክ አልተጠቀመችበትም ነበር።
ዘርፉ እንዲያንሰራራ ፖሊሲ የማውጣት፣ ተቋማትን የማዋቀር፣ አዳዲስ ልማቶችን የማከናወን ሥራ ተከናውኗል፡፡
ከለውጡ ወዲህ በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች የሚገኙ ቅርሶችን ከመጠገን ባለፈ አዳዲስ የቱሪዝም መዳረሻዎች ተገንብተዋል፡፡
የኢትዮጵያ የቱሪዝም ዘርፍ ከፍተኛ እመርታ በማሳየት የሀገሪቱ ዋና የኢኮኖሚ ምንጭ እየሆነ መጥቷል።
የመደመር እሳቤ የኢትዮጵያን የቱሪዝም ዘርፍ ከነበረበት መዘናጋት በማውጣት የሀገሪቱን ብልጽግና ከሚያረጋግጡ ዋና ዋና የኢኮኖሚ ምሰሶዎች አንዱ እንዲሆን አድርጎታል፡፡
መንግሥት ዘርፉን እንደ አንድ ስትራቴጂካዊ የኢኮኖሚ ምሰሶ አድርጎ በመቅረጽ፣ አዳዲስ ግዙፍ መዳረሻዎችን በመገንባት እና ነባር የባህል፣ የታሪክና የተፈጥሮ ጸጋዎችን በማዘመን ረገድ ከፍተኛ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ይገኛል።
ቱሪዝምን ከተፈጥሮ ጥበቃ እና ከማህበረሰብ ልማት ጋር ያቀናጁ የገበታ ለሸገር፣ ገበታ ለሀገር እና ገበታ ለትውልድ ሜጋ ፕሮጀክቶችን መቅረጽና መተግበር ነው።
በርካታ የሀገር ውስጥ እና የውጭ ሀገር ጎብኚዎችን በመሳብ ለሀገሪቱ ገቢና የስራ ዕድል ፈጠራ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል፡፡
ለዘርፉ እድገት መንግሥት በሰጠው ትኩረት አዳዲስ መዳረሻዎችና መሠረተ ልማቶች ተገንብተዋል፡፡
በአዲስ አበባ ከተማ እና በሌሎችም የሀገሪቱ ከተሞች የተከናወኑት የኮሪደር ልማቶች የከተሞችን ውበት በማጎልበት ምቹ ሁኔታን በመፍጠር ቱሪዝሙን ማነቃቃት ተችሏል፡፡
የላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናት፣ የፋሲለደስ ግንብ እና የጁገል ግንብ የመሳሰሉ አንጋፋ ቅርሶችን የመጠበቅና የዕድሳት ሥራዎች በስፋት ተግባራዊ ተደርገዋል፡፡
ከውጭ ጎብኚዎች ባለፈ፣ የሀገር ውስጥ ቱሪዝም ከፍተኛ እድገት እያሳየ ሲሆን፤ ዜጎች ሀገራቸውን እንዲያውቁና እንዲጎበኙ በማድረግ፤ የህዝብ ለህዝብ ትስስርን አጠናክሯል።
የኢትዮጵያ የቱሪዝም ዘርፍ እመርታ የሀገሪቱን አወንታዊ ገጽታ በዓለም አቀፍ ደረጃ በማስተዋወቅ ረገድ የማይተካ ሚና አለው።
የቱሪዝም መዳረሻዎችን በዘመናዊ መንገድ የማልማትና አገልግሎቶችን የማዘመን ሥራዎችም በስፋት እየተሰሩ ነው፡፡
ኢኮኖሚው በብዝሃ ዘርፍ ላይ እንዲመሰረት መደረጉ በቱሪዝም ዘርፍ ያለውን እምቅ አቅም ይበልጥ መጠቀም የሚያስችል ዕድል ፈጥሯል።
በወንድማገኝ ጸጋዬ
17 hours ago
ኢትዮጵያ ለአካባቢ ጥበቃ ያላትን ቁርጠኝነት ለዓለም ያሳየችበት አረንጓዴ ዐሻራ
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 28፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር የግብርና ምርታማነትን ማሳደግን ጨምሮ ዘርፈ ብዙ ሀገራዊ ጠቀሜታዎችን እያበረከተ ነው፡፡
መርሐ ግብሩ የአካባቢ ጥበቃ ሚናውን በጥቂት ዓመታት ብቻ ከፍ አድርጓል፡፡ የአፈር መሸርሸርን በመከላከል እና የደን ሽፋንን በማሳደግ ረገድ ከፍተኛ ውጤት አሳይቷል።
ይህ ንቅናቄ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀሳብ አመንጪነት ከ2011 ዓ.ም ጀምሮ ሲተገበር ቆይቷል። በዚህም የዘንድሮውን ሳይጨምር ከ48 ቢሊየን በላይ ችግኞችን በመትከል ስኬት ተመዝግቦበታል።
የመላው ኢትዮጵያውያን ላብ ውጤት የሆነው አረንጓዴ ዐሻራ የአየር ንብረት ለውጥን እና የተፈጥሮ ሀብት መመናመንን ለመላቀቅ፣ ለምግብ ዋስትናና ለሥራ ዕድል ፈጠራ የተተለመ ትውልድ ተሻጋሪ እቅድ ነው።
የአየር ንብረት ለውጥ ተግዳሮትና የደን መመናመን የአፈር መሸርሸር እና የውሃ አካላት መድረቅ ፈተናዎችን አስከትሎ ነበር፡፡ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር በቁርጠኝነት መተግበሩ የደን መመናመንን በማስቀረት የአየር ንብረት ለውጥ ጫናን ለመቋቋም የሚያስችል አቅም ፈጥሯል።
በዚህም የአፈር መከላት ችግር ቀደም ሲል ከነበረው አንጻር በ50 በመቶ ያህል መቀነስ መቻሉ እና የውሃ አካላት በደለል የመሞላት ችግር መፈታቱ ዘርፈ ብዙ ጥቅም እየሰጠ ይገኛል።
ይህም የምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥ ባለፈ ፍራፍሬዎችን ጨምሮ የተለያዩ የግብርና ምርቶችን ወደ ውጭ የመላክ አቅሟን ለማሳደግ በቅታለች፡፡
የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር ህጻናትን፣ አዛውንቶችን፣ ወጣቶችን እና የመንግሥት ሰራተኞችን ጨምሮ መላውን ህዝብ አሳትፏል፡፡
መርሐ ግብሩ የተፈጥሮ ሀብትን ከመጠበቅ ባለፈ ሰፊ የስራ ዕድል ፈጥሯል።
የመላው ኢትዮጵያውያን የጋራ ላብ ውጤት የሆነው አረንጓዴ አሻራ ዛሬ ላይ የሚታይ ተጨባጭ የለምለም ተፈጥሮ መሠረት ብቻ ሳይሆን ለቀጣዩ ትውልድ ንጹህ አየር፣ ውሃ እና አፈርን የማስተላለፍ ዋስትና ነው።
ይህ ህዝባዊ ንቅናቄ ኢትዮጵያ ለአካባቢ ጥበቃ ያላትን ጽኑ ቁርጠኝነት ለዓለም ያስመሰከረችበት እና አረንጓዴ ኢኮኖሚን እውን ለማድረግ የተጠቀመችበት ታላቅ የድል ምዕራፍ ነው።
በመርሐ ግብሩ የተመዘገበውን ድል የዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ዕውቅና የሰጠው ሲሆን፤ በተለያዩ አጋጣሚዎችም ኢትዮጵያ ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ኢኮኖሚ ለመገንባት የምታደርገውን ጥረት አድንቋል።
የተባበሩት መንግሥታት የአየር ንብረት ጉባኤ (ኮፕ-32) በኢትዮጵያ እንዲዘጋጅ የተወሰነውም ለኢትዮጵያ ጥረት ዕውቅና በመስጠት ነው።
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 28፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር የግብርና ምርታማነትን ማሳደግን ጨምሮ ዘርፈ ብዙ ሀገራዊ ጠቀሜታዎችን እያበረከተ ነው፡፡
መርሐ ግብሩ የአካባቢ ጥበቃ ሚናውን በጥቂት ዓመታት ብቻ ከፍ አድርጓል፡፡ የአፈር መሸርሸርን በመከላከል እና የደን ሽፋንን በማሳደግ ረገድ ከፍተኛ ውጤት አሳይቷል።
ይህ ንቅናቄ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀሳብ አመንጪነት ከ2011 ዓ.ም ጀምሮ ሲተገበር ቆይቷል። በዚህም የዘንድሮውን ሳይጨምር ከ48 ቢሊየን በላይ ችግኞችን በመትከል ስኬት ተመዝግቦበታል።
የመላው ኢትዮጵያውያን ላብ ውጤት የሆነው አረንጓዴ ዐሻራ የአየር ንብረት ለውጥን እና የተፈጥሮ ሀብት መመናመንን ለመላቀቅ፣ ለምግብ ዋስትናና ለሥራ ዕድል ፈጠራ የተተለመ ትውልድ ተሻጋሪ እቅድ ነው።
የአየር ንብረት ለውጥ ተግዳሮትና የደን መመናመን የአፈር መሸርሸር እና የውሃ አካላት መድረቅ ፈተናዎችን አስከትሎ ነበር፡፡ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር በቁርጠኝነት መተግበሩ የደን መመናመንን በማስቀረት የአየር ንብረት ለውጥ ጫናን ለመቋቋም የሚያስችል አቅም ፈጥሯል።
በዚህም የአፈር መከላት ችግር ቀደም ሲል ከነበረው አንጻር በ50 በመቶ ያህል መቀነስ መቻሉ እና የውሃ አካላት በደለል የመሞላት ችግር መፈታቱ ዘርፈ ብዙ ጥቅም እየሰጠ ይገኛል።
ይህም የምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥ ባለፈ ፍራፍሬዎችን ጨምሮ የተለያዩ የግብርና ምርቶችን ወደ ውጭ የመላክ አቅሟን ለማሳደግ በቅታለች፡፡
የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር ህጻናትን፣ አዛውንቶችን፣ ወጣቶችን እና የመንግሥት ሰራተኞችን ጨምሮ መላውን ህዝብ አሳትፏል፡፡
መርሐ ግብሩ የተፈጥሮ ሀብትን ከመጠበቅ ባለፈ ሰፊ የስራ ዕድል ፈጥሯል።
የመላው ኢትዮጵያውያን የጋራ ላብ ውጤት የሆነው አረንጓዴ አሻራ ዛሬ ላይ የሚታይ ተጨባጭ የለምለም ተፈጥሮ መሠረት ብቻ ሳይሆን ለቀጣዩ ትውልድ ንጹህ አየር፣ ውሃ እና አፈርን የማስተላለፍ ዋስትና ነው።
ይህ ህዝባዊ ንቅናቄ ኢትዮጵያ ለአካባቢ ጥበቃ ያላትን ጽኑ ቁርጠኝነት ለዓለም ያስመሰከረችበት እና አረንጓዴ ኢኮኖሚን እውን ለማድረግ የተጠቀመችበት ታላቅ የድል ምዕራፍ ነው።
በመርሐ ግብሩ የተመዘገበውን ድል የዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ዕውቅና የሰጠው ሲሆን፤ በተለያዩ አጋጣሚዎችም ኢትዮጵያ ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ኢኮኖሚ ለመገንባት የምታደርገውን ጥረት አድንቋል።
የተባበሩት መንግሥታት የአየር ንብረት ጉባኤ (ኮፕ-32) በኢትዮጵያ እንዲዘጋጅ የተወሰነውም ለኢትዮጵያ ጥረት ዕውቅና በመስጠት ነው።
1 day ago
የቢሾፍቱ አውሮፕላን ማረፊያ ፕሮጀክት ኢትዮጵያ በአቪየሽን ዘርፍ መሪነቷን እንደታጠናክር ያስችላታል - ሲኤንኤን
***********************
የዓለማችን ታዋቂው የዜና መረብ ሲኤንኤን (CNN) "ኮኔክቲንግ አፍሪካ" በተሰኘው ዝነኛ ፕሮግራሙ፣ የአፍሪካ የአቪዬሽን መሪ የሆነው የኢትዮጵያ አየር መንገድ እየመራው ያለውን ታላቅ የመሠረተ ልማት፣ የኢኮኖሚ እና የቱሪዝም እምርታ በሰፊው ዳስሷል።
ዘገባው እንደ አመላከተው፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ለአህጉሪቱ ምሳሌ የሚሆን የዕድገት ሞተር ከመሆኑም በላይ ኢትዮጵያን የዓለም አቀፍ ትስስር ማዕከል በማድረግ ረገድ ወደ አዲስ እየተሸጋገረ ይገኛል።
ዘገባው ኢትዮጵያ የአቪዬሽን ዘርፏን ዘመናዊ በማድረግ፣ የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣናን (AfCFTA) ተግባራዊነት በማፋጠን እና የተፈጥሮ ሀብቶቿን ለዓለም አስተዋውቃ የቱሪዝም አቅሟን በመገንባት በኩል እያከናወነቻቸው ያሉትን ዐበይት ተግባራት በስፋት አሳይቷል።
በዘገባው ጎልተው ከተካተቱት ዐበይት ጉዳዮች መካከል በ12.5 ቢሊዮን ዶላር ወጪ ግንባታው የተጀመረው እና በአፍሪካ ታሪክ ትልቁ የሆነው የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሜጋ ፕሮጀክት ቀዳሚው ነው።
ይህ ዘመናዊ የአቪዬሽን መንደር የመጀመሪያው ምዕራፍ ሲጠናቀቅ 60 ሚሊዮን፣ ሙሉ በሙሉ ሲጠናቀቅ ደግሞ በዓመት እስከ 110 ሚሊዮን መንገደኞችን የማስተናገድ እና 4 ሚሊዮን ቶን ካርጎ የማጓጓዝ ከፍተኛ አቅም ይኖረዋል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ መስፍን ጣሰው ከሲኤንኤን ዘጋቢ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ፣ አዲሱ አውሮፕላን ማረፊያ አፍሪካውያንን እርስ በእርስ በማስተሳሰር ረገድ የመሪነት ሚናውን እንደሚቀጥል ገልጸዋል።
በተጨማሪም አየር መንገዱ የአፍሪካ ነፃ ንግድ ቀጣናን ስኬታማ ለማድረግ እና አህጉራዊ የንግድ ትስስርን ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር ቁልፍ ሞተር መሆኑን አስረድተዋል።
በዘገባው ላይ እንደተጠቆመው የኢትዮጵያን ተፈጥሯዊና ታሪካዊ ሀብቶች ለዓለም አቀፍ እና ለአህጉራችን ጎብኚዎች ተደራሽ ለማድረግ ዘመናዊ የመሠረተ ልማት ግንባታዎች፣ ደረጃቸውን የጠበቁ የማረፊያ ስፍራዎች እና አዳዲስ የመንገድ ዝርጋታዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ።
ይህም ኢትዮጵያ ከቱሪዝም ዘርፍ የምታገኘውን የኢኮኖሚ ጥቅም ወደ ላቀ ደረጃ የሚያሸጋግር ነው።
የሲኤንኤን ዘገባ የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአቪዬሽን ዘርፍ እያመጣ ያለውን ብሩህ ተስፋ እና በአቪዬሽን መሠረተ ልማት አህጉራዊ መሪነቷን በጽኑ የምታረጋግጥበትን የልማት ጉዞ በግልጽ ያሳየ ነው።
የአፍሪካ ኩራት የሆነው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ሀገራችን የአህጉሪቱ ዋና የንግድ፣ የቱሪዝም እና የኢኮኖሚ መገናኛ ማዕከል በማድረግ ጉዞውን አጠናክሮ ቀጥሏል።
በሔዋን ጌታቸው
#ethiopia #ebc #bishoftuairport #ethiopianairlines #connectingafrica #cnn
***********************
የዓለማችን ታዋቂው የዜና መረብ ሲኤንኤን (CNN) "ኮኔክቲንግ አፍሪካ" በተሰኘው ዝነኛ ፕሮግራሙ፣ የአፍሪካ የአቪዬሽን መሪ የሆነው የኢትዮጵያ አየር መንገድ እየመራው ያለውን ታላቅ የመሠረተ ልማት፣ የኢኮኖሚ እና የቱሪዝም እምርታ በሰፊው ዳስሷል።
ዘገባው እንደ አመላከተው፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ለአህጉሪቱ ምሳሌ የሚሆን የዕድገት ሞተር ከመሆኑም በላይ ኢትዮጵያን የዓለም አቀፍ ትስስር ማዕከል በማድረግ ረገድ ወደ አዲስ እየተሸጋገረ ይገኛል።
ዘገባው ኢትዮጵያ የአቪዬሽን ዘርፏን ዘመናዊ በማድረግ፣ የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣናን (AfCFTA) ተግባራዊነት በማፋጠን እና የተፈጥሮ ሀብቶቿን ለዓለም አስተዋውቃ የቱሪዝም አቅሟን በመገንባት በኩል እያከናወነቻቸው ያሉትን ዐበይት ተግባራት በስፋት አሳይቷል።
በዘገባው ጎልተው ከተካተቱት ዐበይት ጉዳዮች መካከል በ12.5 ቢሊዮን ዶላር ወጪ ግንባታው የተጀመረው እና በአፍሪካ ታሪክ ትልቁ የሆነው የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሜጋ ፕሮጀክት ቀዳሚው ነው።
ይህ ዘመናዊ የአቪዬሽን መንደር የመጀመሪያው ምዕራፍ ሲጠናቀቅ 60 ሚሊዮን፣ ሙሉ በሙሉ ሲጠናቀቅ ደግሞ በዓመት እስከ 110 ሚሊዮን መንገደኞችን የማስተናገድ እና 4 ሚሊዮን ቶን ካርጎ የማጓጓዝ ከፍተኛ አቅም ይኖረዋል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ መስፍን ጣሰው ከሲኤንኤን ዘጋቢ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ፣ አዲሱ አውሮፕላን ማረፊያ አፍሪካውያንን እርስ በእርስ በማስተሳሰር ረገድ የመሪነት ሚናውን እንደሚቀጥል ገልጸዋል።
በተጨማሪም አየር መንገዱ የአፍሪካ ነፃ ንግድ ቀጣናን ስኬታማ ለማድረግ እና አህጉራዊ የንግድ ትስስርን ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር ቁልፍ ሞተር መሆኑን አስረድተዋል።
በዘገባው ላይ እንደተጠቆመው የኢትዮጵያን ተፈጥሯዊና ታሪካዊ ሀብቶች ለዓለም አቀፍ እና ለአህጉራችን ጎብኚዎች ተደራሽ ለማድረግ ዘመናዊ የመሠረተ ልማት ግንባታዎች፣ ደረጃቸውን የጠበቁ የማረፊያ ስፍራዎች እና አዳዲስ የመንገድ ዝርጋታዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ።
ይህም ኢትዮጵያ ከቱሪዝም ዘርፍ የምታገኘውን የኢኮኖሚ ጥቅም ወደ ላቀ ደረጃ የሚያሸጋግር ነው።
የሲኤንኤን ዘገባ የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአቪዬሽን ዘርፍ እያመጣ ያለውን ብሩህ ተስፋ እና በአቪዬሽን መሠረተ ልማት አህጉራዊ መሪነቷን በጽኑ የምታረጋግጥበትን የልማት ጉዞ በግልጽ ያሳየ ነው።
የአፍሪካ ኩራት የሆነው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ሀገራችን የአህጉሪቱ ዋና የንግድ፣ የቱሪዝም እና የኢኮኖሚ መገናኛ ማዕከል በማድረግ ጉዞውን አጠናክሮ ቀጥሏል።
በሔዋን ጌታቸው
#ethiopia #ebc #bishoftuairport #ethiopianairlines #connectingafrica #cnn
1 day ago
ኢትዮጵያ ለዓለም ያስተማረችው አዲስ ታሪክ
****************
ትላንት በመላው ኢትዮጵያ በተካሄደው ታሪካዊ የአንድ ጀምበር የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር ኢትዮጵያ በ12 ሰዓታት ውስጥ ለመትከል ካቀደችው 800 ሚሊዮን ችግኝ 805 ሚሊዮን ችግኞችን በመትከል አዲስ የዓለም አቀፍ ሥነ ምህዳር ጥበቃ ታሪክ አስመዝግባለች።
ከማለዳው ጀምሮ በመላው ኢትዮጵያ በሚገኙ የመትከያ ስፍራዎች ወጣቶች፣ የመንግሥት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች፣ የዲፕሎማቲክ ማኅበረሰብ አባላት እና ታዋቂ ግለሰቦች በተገኙበት የተካሄደው ይህ ታላቅ ሕዝባዊ ንቅናቄ ኢትዮጵያውያን ለሀገራቸው ተፈጥሮአዊ ህልውና እና ለቀጣዩ ትውልድ አረንጓዴ ምድር ያላቸውን ቁርጠኝነት በተግባር ያረጋገጡበት ሆኗል።
ኢትዮጵያ ካቀደችው በላይ 805 ሚሊዮን ችግኞችን በመትከል ባስመዘገበችው በዚህ ታላቅ ስኬት ለዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ጠንካራ መልእክቶችን አስተላልፋለች።
የአየር ንብረት መዛባትን ለመከላከል የሚደረገው ጥረት በመግለጫዎች እና በኮንፈረንሶች ብቻ ሳይሆን በተግባር መሬት ላይ በሚወርዱ ግዙፍ ሕዝባዊ ሥራዎች መመራት እንዳለበት በተግባር የተደገፈ መሪነቷን አሳይታለች።
በሌላ በኩል ሀገራችን የራሷን የደን ሽፋን ከማሳደግ እና የደረቁ የውኃ አካላትን ከመመለስ ባለፈ ለጎረቤት ሀገራት ችግኞችን በማካፈል በቀጣናው አረንጓዴ ኢኮኖሚን ለመገንባት የምታደርገውን ጥረት አጠናክራ እንደምትቀጥል አረጋግጣለች።
ኢትዮጵያ በራሷ አቅም እና በሕዝቧ ንቅናቄ ትልቅ ሀገራዊ ሀላፊነቷን መወጣቷን በመግለጽ የበለፀጉ ሀገራት እና የዓለም አቀፍ አካባቢ ጥበቃ ተቋማት ለአየር ንብረት ለውጥ መከላከል የገቡትን የፋይናንስ እና የቴክኖሎጂ ድጋፍ ቃል በተግባር እንዲወጡ በድፍረት እንድትሞግት ትልቅ የዲፕሎማሲ ሞራል እና አቅም ፈጥሮላታል።
ይህ ታሪካዊ ስኬት ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ ደረጃ የተጣለባትን እምነት የሚያጸና ሲሆን፣ ሀገራችን በታላላቅ የዓለም አቀፍ የአየር ንብረት ጉባኤዎች ላይ በዘርፉ ያላትን የላቀ የሞራል ልዕልና እና ተደማጭነት ለዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ዳግም ያስመሰከረ ነው።
የተመዘገበው 805 ሚሊዮን ችግኝ ተከላ ስኬት የዛሬን የተፈጥሮ ቁስል እያከመ፣ የነገዋን ኢትዮጵያ እና የዓለምን ሥነ ምህዳር ለመጠበቅ በተግባር የተጻፈ ታሪካዊ የአረንጓዴ ዐሻራ ምዕራፍ ነው።
በሃና ምንዳሁን
#ethiopia #ebc #ebcdotstream #greenlegacy #planthope #climateresilience #ethiopiarising
****************
ትላንት በመላው ኢትዮጵያ በተካሄደው ታሪካዊ የአንድ ጀምበር የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር ኢትዮጵያ በ12 ሰዓታት ውስጥ ለመትከል ካቀደችው 800 ሚሊዮን ችግኝ 805 ሚሊዮን ችግኞችን በመትከል አዲስ የዓለም አቀፍ ሥነ ምህዳር ጥበቃ ታሪክ አስመዝግባለች።
ከማለዳው ጀምሮ በመላው ኢትዮጵያ በሚገኙ የመትከያ ስፍራዎች ወጣቶች፣ የመንግሥት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች፣ የዲፕሎማቲክ ማኅበረሰብ አባላት እና ታዋቂ ግለሰቦች በተገኙበት የተካሄደው ይህ ታላቅ ሕዝባዊ ንቅናቄ ኢትዮጵያውያን ለሀገራቸው ተፈጥሮአዊ ህልውና እና ለቀጣዩ ትውልድ አረንጓዴ ምድር ያላቸውን ቁርጠኝነት በተግባር ያረጋገጡበት ሆኗል።
ኢትዮጵያ ካቀደችው በላይ 805 ሚሊዮን ችግኞችን በመትከል ባስመዘገበችው በዚህ ታላቅ ስኬት ለዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ጠንካራ መልእክቶችን አስተላልፋለች።
የአየር ንብረት መዛባትን ለመከላከል የሚደረገው ጥረት በመግለጫዎች እና በኮንፈረንሶች ብቻ ሳይሆን በተግባር መሬት ላይ በሚወርዱ ግዙፍ ሕዝባዊ ሥራዎች መመራት እንዳለበት በተግባር የተደገፈ መሪነቷን አሳይታለች።
በሌላ በኩል ሀገራችን የራሷን የደን ሽፋን ከማሳደግ እና የደረቁ የውኃ አካላትን ከመመለስ ባለፈ ለጎረቤት ሀገራት ችግኞችን በማካፈል በቀጣናው አረንጓዴ ኢኮኖሚን ለመገንባት የምታደርገውን ጥረት አጠናክራ እንደምትቀጥል አረጋግጣለች።
ኢትዮጵያ በራሷ አቅም እና በሕዝቧ ንቅናቄ ትልቅ ሀገራዊ ሀላፊነቷን መወጣቷን በመግለጽ የበለፀጉ ሀገራት እና የዓለም አቀፍ አካባቢ ጥበቃ ተቋማት ለአየር ንብረት ለውጥ መከላከል የገቡትን የፋይናንስ እና የቴክኖሎጂ ድጋፍ ቃል በተግባር እንዲወጡ በድፍረት እንድትሞግት ትልቅ የዲፕሎማሲ ሞራል እና አቅም ፈጥሮላታል።
ይህ ታሪካዊ ስኬት ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ ደረጃ የተጣለባትን እምነት የሚያጸና ሲሆን፣ ሀገራችን በታላላቅ የዓለም አቀፍ የአየር ንብረት ጉባኤዎች ላይ በዘርፉ ያላትን የላቀ የሞራል ልዕልና እና ተደማጭነት ለዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ዳግም ያስመሰከረ ነው።
የተመዘገበው 805 ሚሊዮን ችግኝ ተከላ ስኬት የዛሬን የተፈጥሮ ቁስል እያከመ፣ የነገዋን ኢትዮጵያ እና የዓለምን ሥነ ምህዳር ለመጠበቅ በተግባር የተጻፈ ታሪካዊ የአረንጓዴ ዐሻራ ምዕራፍ ነው።
በሃና ምንዳሁን
#ethiopia #ebc #ebcdotstream #greenlegacy #planthope #climateresilience #ethiopiarising
2 days ago
ከቃል ባሻገር የታየ ሀገራዊ ብቃት፡ ትላልቅ ህልሞችን የማሳካት ታሪካዊ ጉዞ
************************
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፣ “የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር ኢትዮጵያ ትላልቅ ነገሮችን አቅዳ ሕዝቦቿን አስተባብራ ማሳካት እንደምትችል ማሳያ ነው" ሲሉ የተናገሩት ሀሳብ በትላንትናው ዕለት መላ ኢትዮጵያንን ባንቀሳቀሰው ግዙፍ ንቅናቄ በተግባር ተረጋገጧል።
ኢትዮጵያውያን ከጫፍ እስከ ጫፍ በአንድ ልብ ተነስተው ያከናወኑት የችግኝ ተከላ ሀገራችን በጽናት ከተነሳች እና ሕዝቧን በአንድነት አስተባብራ ከተንቀሳቀሰች ማንኛውንም ግዙፍ ሀገራዊ ህልም ማሳካት እንደምትችል ለዓለም ያስመሰከረችበት ታሪካዊ ዕለት ሆኗል።
በዕለቱ የተከናወነው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር የችግኝ ተከላ ሂደት ብቻ ሳይሆን፣ የሕዝብን አቅም እና ቁርጠኝነት ያሳየ አዲስ የታሪክ ምዕራፍ ነው።
ከማለዳው ጀምሮ በየተራራው፣ በየሸለቆው እና በየከተሞች አደባባይ የታየው ሕዝባዊ መነቃቃት የሀገራዊ ኅብረታችንን ጥንካሬ በግልጽ ያሳየ ነበር።
ይህ በትላንትናው ዕለት በየቦታው የተተከለው አረንጓዴ ዐሻራ ሀገራችን ለአየር ንብረት ለውጥ የማትበገር፣ በምግብ ራሷን የቻለች እና ለተፈጥሮ ሀብቷ ተቆርቋሪ የሆነች ኢትዮጵያን የመገንባት ትልቅ ራእይ በተግባር የተተረጎመበት ነው።
ይህ ታላቅ ስኬት ሙሉ የሚሆነው ከመትከል ባሻገር በሚደረገው ዘላቂ ጥረት መሆኑን መገንዘብ ያስፈልጋል።
ችግኝ መትከል የመጀመሪያው እና ወሳኙ እርምጃ ቢሆንም፣ ዋናውና ትልቁ ትኩረታችን መሆን ያለበት በተተከሉት ችግኞች እንክብካቤ ላይ ነው። እያንዳንዷ የተተከለች ችግኝ ተንከባካቢ እና ጠባቂ ሊኖራት ይገባል።
ችግኞቹ ፀድቀው፣ አድገው እና ጥላ እና ፍሬ ሆነው እስኪታዩ ድረስ የማኅበረሰቡ፣ የተቋማት እና የየአካባቢው ዜጎች የቅርብ ክትትል ሊደረግላቸው ይገባል።
የዚህ ኅበረታችን የመጨረሻው ስኬት የሚለካው በኅበረት ወጥተን ችግኞቹን እንደተከልናቸው ሁሉ አድገው በጸደቁት እና የአካባቢውን ሥነ-ምህዳር በቀየሩት ዛፎች መጠን ነው::
ዛሬ በየምድሩ የተተከሉት ሚሊዮን ችግኞች የነገዋ ኢትዮጵያ የኢኮኖሚ እና የአካባቢ ጥበቃ ሀብቶች ናቸው።
በመሆኑም ከዚህ የተከላ ንቅናቄ ማጠቃለያ በኋላ እያንዳንዱ ዜጋ የተተከሉትን ችግኞች የመጠበቅ፣ የመንከባከብ እና የማሳደግ ሀገራዊ ኃላፊነቱን አጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል።
ዛሬ በላባችን ያራሰነው አፈር እና የተከልነው ችግኝ ነገ ለሀገራችን ለምለምነት፣ ለንጹህ አየር እና ለቀጣዩ ትውልድ አስተማማኝ ሕይወት ዋስትና ሆኖ ይኖራል።
በሔዋን ጌታቸው
#ethiopia #ebc #greenlegacyethiopia #plantingtonurturing #sustainableethiopia
************************
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፣ “የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር ኢትዮጵያ ትላልቅ ነገሮችን አቅዳ ሕዝቦቿን አስተባብራ ማሳካት እንደምትችል ማሳያ ነው" ሲሉ የተናገሩት ሀሳብ በትላንትናው ዕለት መላ ኢትዮጵያንን ባንቀሳቀሰው ግዙፍ ንቅናቄ በተግባር ተረጋገጧል።
ኢትዮጵያውያን ከጫፍ እስከ ጫፍ በአንድ ልብ ተነስተው ያከናወኑት የችግኝ ተከላ ሀገራችን በጽናት ከተነሳች እና ሕዝቧን በአንድነት አስተባብራ ከተንቀሳቀሰች ማንኛውንም ግዙፍ ሀገራዊ ህልም ማሳካት እንደምትችል ለዓለም ያስመሰከረችበት ታሪካዊ ዕለት ሆኗል።
በዕለቱ የተከናወነው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር የችግኝ ተከላ ሂደት ብቻ ሳይሆን፣ የሕዝብን አቅም እና ቁርጠኝነት ያሳየ አዲስ የታሪክ ምዕራፍ ነው።
ከማለዳው ጀምሮ በየተራራው፣ በየሸለቆው እና በየከተሞች አደባባይ የታየው ሕዝባዊ መነቃቃት የሀገራዊ ኅብረታችንን ጥንካሬ በግልጽ ያሳየ ነበር።
ይህ በትላንትናው ዕለት በየቦታው የተተከለው አረንጓዴ ዐሻራ ሀገራችን ለአየር ንብረት ለውጥ የማትበገር፣ በምግብ ራሷን የቻለች እና ለተፈጥሮ ሀብቷ ተቆርቋሪ የሆነች ኢትዮጵያን የመገንባት ትልቅ ራእይ በተግባር የተተረጎመበት ነው።
ይህ ታላቅ ስኬት ሙሉ የሚሆነው ከመትከል ባሻገር በሚደረገው ዘላቂ ጥረት መሆኑን መገንዘብ ያስፈልጋል።
ችግኝ መትከል የመጀመሪያው እና ወሳኙ እርምጃ ቢሆንም፣ ዋናውና ትልቁ ትኩረታችን መሆን ያለበት በተተከሉት ችግኞች እንክብካቤ ላይ ነው። እያንዳንዷ የተተከለች ችግኝ ተንከባካቢ እና ጠባቂ ሊኖራት ይገባል።
ችግኞቹ ፀድቀው፣ አድገው እና ጥላ እና ፍሬ ሆነው እስኪታዩ ድረስ የማኅበረሰቡ፣ የተቋማት እና የየአካባቢው ዜጎች የቅርብ ክትትል ሊደረግላቸው ይገባል።
የዚህ ኅበረታችን የመጨረሻው ስኬት የሚለካው በኅበረት ወጥተን ችግኞቹን እንደተከልናቸው ሁሉ አድገው በጸደቁት እና የአካባቢውን ሥነ-ምህዳር በቀየሩት ዛፎች መጠን ነው::
ዛሬ በየምድሩ የተተከሉት ሚሊዮን ችግኞች የነገዋ ኢትዮጵያ የኢኮኖሚ እና የአካባቢ ጥበቃ ሀብቶች ናቸው።
በመሆኑም ከዚህ የተከላ ንቅናቄ ማጠቃለያ በኋላ እያንዳንዱ ዜጋ የተተከሉትን ችግኞች የመጠበቅ፣ የመንከባከብ እና የማሳደግ ሀገራዊ ኃላፊነቱን አጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል።
ዛሬ በላባችን ያራሰነው አፈር እና የተከልነው ችግኝ ነገ ለሀገራችን ለምለምነት፣ ለንጹህ አየር እና ለቀጣዩ ትውልድ አስተማማኝ ሕይወት ዋስትና ሆኖ ይኖራል።
በሔዋን ጌታቸው
#ethiopia #ebc #greenlegacyethiopia #plantingtonurturing #sustainableethiopia
2 days ago
የዘመናችን ሉዓላዊነት፡ ከድንበር ጥበቃ እስከ ኢኮኖሚያዊና ዲጂታል ልዕልና
*******************
( የዕለቱ መልዕክት)
ትናንት የሀገር ዳር ድንበር በጀግኖች ደምና አጥንት ይጠበቅ ነበር። ዛሬ ግን የዓለማችን የጂኦ-ፖለቲካ መልክ እና የኃይል አሰላለፍ መሰረታዊ ለውጥ ሲያስተናግድ፣ የሉዓላዊነት ትርጓሜም እጅግ ጥልቅ የሆነ አዲስ ገጽታን ተላብሷል።
በ21ኛው ክፍለ ዘመን የኢትዮጵያ ሉዓላዊነት እና የህልውና ዋስትና የሚረጋገጠው ጂኦግራፊያዊ ድንበርን በጦር መሣሪያ በመጠበቅ ብቻ ሳይሆን በስንዴ ማሳዎቻችን ስፋት፣ በፋብሪካዎቻችን የማምረት አቅም እንዲሁም በዲጂታል ቴክኖሎጂ ብቃታችን ጭምር ነው።
እውነተኛ ነፃነት ማለት የራስን ትርክት በራስ አቅም መጻፍ መቻል፣ የራስን ህዝብ በራስ አቅም መመገብ እና የሀገርን ጉዳይ ያለ አንዳች የውጭ ጫና መወሰን መቻል ማለት ነው።
ይህ ሉዓለዊነት ከእርዳታ ጥገኝነት እና ከተረጂነት አዘቅት ተላቆ በምግብ ራስን መቻልን፣ ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ አቅም ማምረትን እና በከንቱ የሚባክኑ የተፈጥሮ ጸጋዎቻችንን ወደ ሀገራዊ ሀብት መቀየርን ማዕከል ያደረገ ነው።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) "ደሃ አይከበርም፤ እየለመነ የሚኖር ሀገር አይከበርም" ሲሉ የተናገሩት መራር ሀቅ፣ የዘመናችንን የሉዓላዊነት ትግል ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ ነው። ክብራችን በዓለም አቀፍ መድረክ ላይ ደምቆ የሚታየው፣ ቃላችንም የሚሰማው ፖሊሲዎቻችንን ያለማንም ጣልቃ ገብነት ማስፈጸም የሚያስችል የኢኮኖሚ ጡንቻ ስንገነባ ብቻ መሆኑን ይህ አዲስ እሳቤ ያስገነዝበናል።
ይህ ሁለንተናዊ የኢኮኖሚ እና የቴክኖሎጂ ሉዓላዊነት እርስበርስ በተሳሰሩ ጠንካራ ምሰሶዎች ላይ የቆመ ነው። የግብርናው ዘርፍ ዜጎችን ከረሃብ ከመታደግ አልፎ፣ ሀገርን በእርዳታ ስም ከሚመጣ የፖለቲካ ተጽዕኖ እና የውጭ ጫና ነጻ የማውጣት አቅም አለው።
ከዚህ ጎን ለጎን አምራች ኢንዱስትሪውና ማዕድን ልማቱ የውጭ ምንዛሬን በማስገኘት ሀገራዊ ሜጋ ፕሮጀክቶቻችንን በራሳችን አቅም እንድንገነባና ኢኮኖሚያችን እንዲጠናከሩ እያደረጉ ይገኛሉ። የቱሪዝም ዘርፉ የብሔራዊ ገጽታችንን ከመገንባት ባሻገር ባህላችንን ለዓለም የምናስተዋውቅበት የሶፍት ፓወር መሣሪያችን ሲሆን የዲጂታል ኢኮኖሚው ደግሞ ከዘመኑ የቴክኖሎጂ ፍጥነት ጋር እኩል እንድንራመድ የሚያደርገን የህልውናችን ወሳኝ ቁልፍ ሆኗል።
የታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ የሉኣላዊነታችን መከበር ትልቁ ማሳያ ነው። ዓለም አቀፍ ጫናዎችን ተቋቁመን ግድቡን ከዳር ማድረሳችን፣ ወደ ብሪክስ (BRICS) አባልነት መቀላቀላችን እና የባህር በር ጥያቄያችንን በዲፕሎማሲያዊ መንገድ ለማሳካት የምናደርገው ትጋት ሀገራችን በዓለም አቀፍ መድረክ ያላትን ተሰሚነት እና ሉዓላዊ ክብሯን በተጨባጭ የሚያሳዩም ናቸው።
ይሁን እንጂ፣ እነዚህ ታላላቅ ሀገራዊ ስኬቶችና የዲፕሎማሲ ድሎች ዘላቂና ሙሉ ትርጉም የሚኖራቸው በውስጣችን ሰላምና ሀገራዊ መግባባት ሲሰፍን ብቻ መሆኑን መዘንጋት የለብንም። የልዩነት ግንቦችን አፍርሰን በጠረጴዛ ዙሪያ በሀገራዊ ምክክር ካልተወያየን እንዲሁም የጋራ ጠላታችን በሆነው ድህነት ላይ በአንድነት ካልዘመትን፣ የጀመርነውን የብልጽግና ጉዞ ማሳካትና ሉዓላዊነታችንን ከውስጥም ከውጭም ማስጠበቅ እጅግ ይከብዳል። የኢኮኖሚና የዲጂታል ልዕልናን ለማረጋገጥ መነሻው የውስጥ ሰላምና የአንድነት መንፈስ ነው።
በሌላ በኩል ደግሞ ይህን ሁለንተናዊ የልማት ጉዞ እውን ለማድረግ የሀገርን ሉዓላዊነት እና የሕዝባችንን ሰላም ለማስጠበቅ ሌሊትና ቀን የሚተጋው፣ በቆራጥነትና በጀግንነት የተገነባው መከላከያ ሠራዊታችን ሚና በጉልህ የሚጠቀስ ነዉ፡፡
ሠራዊቱ ለሀገሩና ለህዝቡ ሲል ዛሬም ይፋለማል፣ ይዋደቃል፣ የተከበረ ህይወቱንም ይሰጣል። ይህ ሠራዊት ሀገሩን ከውጭና ከውስጥ ፀረ-ሰላም ኃይሎች በመጠበቅ የሉዓላዊነታችን ጠንካራ ዘብ በመሆን ለልማታችን ምቹ ሁኔታን ይፈጥራል።
የሠራዊቱን የጀግንነት ፈለግ በመከተል ሕዝብ በአንድነት ሲቆም፣ አገርን ከጠላት መጠበቅና ወደ ብልጽግና ማሻገር ይቻላል። ስለዚህም የሀገርን ድንበርና ሰላም በንቃት መጠበቅ እንዲሁም ለጸጥታ አካላት ጠንካራ ድጋፍና አጋርነት ማሳየት የሁሉም ዜጋ ግዴታ ነው።
ስለሆነም አሁን ጊዜው ታሪካዊ ጀግንነታችንን ወደ አዲስ ምዕራፍ የምናሸጋግርበት ወቅት ነው። ሀገራዊ ሉዓላዊነታችንን ዘላቂ ለማድረግ፣ ሁለንተናዊ ብልጽግናችንን ለማረጋገጥ እንዲሁም ትግላችንን ከጦር ሜዳ ወደ ዲጂታል ፈጠራ፣ ከተረጂነት ወደ አምራችነት እና ወደ ጠንካራ የስራ ባህል የምናሸጋግርበት ወሳኝ የለውጥ ዘመን ላይ እንገኛለን። የትናንት አባቶቻችን በደማቸው ያቆዩልንን ነጻነት፣ ዛሬ በላባችን፣ በእውቀታችን እና በፈጠራ ክህሎታችን ልናደምቀው ግድ ይለናል!
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
*******************
( የዕለቱ መልዕክት)
ትናንት የሀገር ዳር ድንበር በጀግኖች ደምና አጥንት ይጠበቅ ነበር። ዛሬ ግን የዓለማችን የጂኦ-ፖለቲካ መልክ እና የኃይል አሰላለፍ መሰረታዊ ለውጥ ሲያስተናግድ፣ የሉዓላዊነት ትርጓሜም እጅግ ጥልቅ የሆነ አዲስ ገጽታን ተላብሷል።
በ21ኛው ክፍለ ዘመን የኢትዮጵያ ሉዓላዊነት እና የህልውና ዋስትና የሚረጋገጠው ጂኦግራፊያዊ ድንበርን በጦር መሣሪያ በመጠበቅ ብቻ ሳይሆን በስንዴ ማሳዎቻችን ስፋት፣ በፋብሪካዎቻችን የማምረት አቅም እንዲሁም በዲጂታል ቴክኖሎጂ ብቃታችን ጭምር ነው።
እውነተኛ ነፃነት ማለት የራስን ትርክት በራስ አቅም መጻፍ መቻል፣ የራስን ህዝብ በራስ አቅም መመገብ እና የሀገርን ጉዳይ ያለ አንዳች የውጭ ጫና መወሰን መቻል ማለት ነው።
ይህ ሉዓለዊነት ከእርዳታ ጥገኝነት እና ከተረጂነት አዘቅት ተላቆ በምግብ ራስን መቻልን፣ ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ አቅም ማምረትን እና በከንቱ የሚባክኑ የተፈጥሮ ጸጋዎቻችንን ወደ ሀገራዊ ሀብት መቀየርን ማዕከል ያደረገ ነው።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) "ደሃ አይከበርም፤ እየለመነ የሚኖር ሀገር አይከበርም" ሲሉ የተናገሩት መራር ሀቅ፣ የዘመናችንን የሉዓላዊነት ትግል ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ ነው። ክብራችን በዓለም አቀፍ መድረክ ላይ ደምቆ የሚታየው፣ ቃላችንም የሚሰማው ፖሊሲዎቻችንን ያለማንም ጣልቃ ገብነት ማስፈጸም የሚያስችል የኢኮኖሚ ጡንቻ ስንገነባ ብቻ መሆኑን ይህ አዲስ እሳቤ ያስገነዝበናል።
ይህ ሁለንተናዊ የኢኮኖሚ እና የቴክኖሎጂ ሉዓላዊነት እርስበርስ በተሳሰሩ ጠንካራ ምሰሶዎች ላይ የቆመ ነው። የግብርናው ዘርፍ ዜጎችን ከረሃብ ከመታደግ አልፎ፣ ሀገርን በእርዳታ ስም ከሚመጣ የፖለቲካ ተጽዕኖ እና የውጭ ጫና ነጻ የማውጣት አቅም አለው።
ከዚህ ጎን ለጎን አምራች ኢንዱስትሪውና ማዕድን ልማቱ የውጭ ምንዛሬን በማስገኘት ሀገራዊ ሜጋ ፕሮጀክቶቻችንን በራሳችን አቅም እንድንገነባና ኢኮኖሚያችን እንዲጠናከሩ እያደረጉ ይገኛሉ። የቱሪዝም ዘርፉ የብሔራዊ ገጽታችንን ከመገንባት ባሻገር ባህላችንን ለዓለም የምናስተዋውቅበት የሶፍት ፓወር መሣሪያችን ሲሆን የዲጂታል ኢኮኖሚው ደግሞ ከዘመኑ የቴክኖሎጂ ፍጥነት ጋር እኩል እንድንራመድ የሚያደርገን የህልውናችን ወሳኝ ቁልፍ ሆኗል።
የታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ የሉኣላዊነታችን መከበር ትልቁ ማሳያ ነው። ዓለም አቀፍ ጫናዎችን ተቋቁመን ግድቡን ከዳር ማድረሳችን፣ ወደ ብሪክስ (BRICS) አባልነት መቀላቀላችን እና የባህር በር ጥያቄያችንን በዲፕሎማሲያዊ መንገድ ለማሳካት የምናደርገው ትጋት ሀገራችን በዓለም አቀፍ መድረክ ያላትን ተሰሚነት እና ሉዓላዊ ክብሯን በተጨባጭ የሚያሳዩም ናቸው።
ይሁን እንጂ፣ እነዚህ ታላላቅ ሀገራዊ ስኬቶችና የዲፕሎማሲ ድሎች ዘላቂና ሙሉ ትርጉም የሚኖራቸው በውስጣችን ሰላምና ሀገራዊ መግባባት ሲሰፍን ብቻ መሆኑን መዘንጋት የለብንም። የልዩነት ግንቦችን አፍርሰን በጠረጴዛ ዙሪያ በሀገራዊ ምክክር ካልተወያየን እንዲሁም የጋራ ጠላታችን በሆነው ድህነት ላይ በአንድነት ካልዘመትን፣ የጀመርነውን የብልጽግና ጉዞ ማሳካትና ሉዓላዊነታችንን ከውስጥም ከውጭም ማስጠበቅ እጅግ ይከብዳል። የኢኮኖሚና የዲጂታል ልዕልናን ለማረጋገጥ መነሻው የውስጥ ሰላምና የአንድነት መንፈስ ነው።
በሌላ በኩል ደግሞ ይህን ሁለንተናዊ የልማት ጉዞ እውን ለማድረግ የሀገርን ሉዓላዊነት እና የሕዝባችንን ሰላም ለማስጠበቅ ሌሊትና ቀን የሚተጋው፣ በቆራጥነትና በጀግንነት የተገነባው መከላከያ ሠራዊታችን ሚና በጉልህ የሚጠቀስ ነዉ፡፡
ሠራዊቱ ለሀገሩና ለህዝቡ ሲል ዛሬም ይፋለማል፣ ይዋደቃል፣ የተከበረ ህይወቱንም ይሰጣል። ይህ ሠራዊት ሀገሩን ከውጭና ከውስጥ ፀረ-ሰላም ኃይሎች በመጠበቅ የሉዓላዊነታችን ጠንካራ ዘብ በመሆን ለልማታችን ምቹ ሁኔታን ይፈጥራል።
የሠራዊቱን የጀግንነት ፈለግ በመከተል ሕዝብ በአንድነት ሲቆም፣ አገርን ከጠላት መጠበቅና ወደ ብልጽግና ማሻገር ይቻላል። ስለዚህም የሀገርን ድንበርና ሰላም በንቃት መጠበቅ እንዲሁም ለጸጥታ አካላት ጠንካራ ድጋፍና አጋርነት ማሳየት የሁሉም ዜጋ ግዴታ ነው።
ስለሆነም አሁን ጊዜው ታሪካዊ ጀግንነታችንን ወደ አዲስ ምዕራፍ የምናሸጋግርበት ወቅት ነው። ሀገራዊ ሉዓላዊነታችንን ዘላቂ ለማድረግ፣ ሁለንተናዊ ብልጽግናችንን ለማረጋገጥ እንዲሁም ትግላችንን ከጦር ሜዳ ወደ ዲጂታል ፈጠራ፣ ከተረጂነት ወደ አምራችነት እና ወደ ጠንካራ የስራ ባህል የምናሸጋግርበት ወሳኝ የለውጥ ዘመን ላይ እንገኛለን። የትናንት አባቶቻችን በደማቸው ያቆዩልንን ነጻነት፣ ዛሬ በላባችን፣ በእውቀታችን እና በፈጠራ ክህሎታችን ልናደምቀው ግድ ይለናል!
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
Sponsored by
Surafel
2 days ago
ከዛፎች ጥላ ስር
ትናንት የተከልናቸው ችግኞች አድገው ጥላ ሆነውን፣ ከስሮቻቸው ተሰብስበን ጉዳዮቻችንን ተወያይተንባቸዋል። አረንጓዴ ዐሻራ ፍሬ አፍርቶ፣ የህይወት እስትንፋስ የሆነውን ተፈጥሮን ዳግም አስነስቶልናል።
በእነዚህ የዛፍ ጥላዎች ስር ሆነን፣ ከባቢ አየራችን እንዴት እንደተቀየረ መመስከር ጀምረናል። የተራቆቱ ተራሮቻችን አረንጓዴ ለብሰው የአፈር መሸርሸር ቆሟል፤ የጠፉ ምንጮቻችን ፈልቀው የተፈጥሮ የውሃ ዑደታችንን በሚገርም ሁኔታ መልሰነዋል።
ውይይታችን ወደ ኢኮኖሚያዊ ትሩፋቶቻችን ሄዶ፣ የተከልናቸው የፍራፍሬ እና የጥምር ደን ግብርና ችግኞች የምግብ ዋስትናችንን እያረጋገጡልን መሆኑን አንስተናል። ለወጣቶቻችን የስራ እድል ከመፍጠር ባለፈ፣ የቤተሰብ ገቢያችንን በከፍተኛ ደረጃ አሳድገንበታል።
ይህ አረንጓዴ ጉዞ ማህበራዊ ትስስራችንንም እጅግ አጠናክሮታል።
በክረምት ዝናብና ጭቃው ሳይበግረን አብረን የተከልነው እያንዳንዱ ችግኝ፣ የብሔራዊ አንድነታችንና የጋራ ራዕያችን ህያው ሀውልት ሆኖ ዛሬም በመካከላችን የፍቅር ጥላ ዘርግቷል።
እያደረግን ያለነው የአየር ንብረት ለውጥን የመከላከል ትግል ለዓለም ትልቅ ትምህርት ሆኗል። ከድርቅ ስጋት ተላቀን፣ ለምድራችን ጤንነት ግንባር ቀደም ጠበቆች በመሆናችን ልባዊ ኩራት ይሰማናል።
ከዛፎቹ ጥላ ስር የምንነሳው ለቀጣዩ ትውልድ የተሻለች እና የበለጸገች ሀገር ለማስረከብ ቃል በመግባት ነው። አረንጓዴ ዐሻራችን የህልውናችን መሰረት ሆኗል፡፡
ትናንት የተከልናቸው ችግኞች አድገው ጥላ ሆነውን፣ ከስሮቻቸው ተሰብስበን ጉዳዮቻችንን ተወያይተንባቸዋል። አረንጓዴ ዐሻራ ፍሬ አፍርቶ፣ የህይወት እስትንፋስ የሆነውን ተፈጥሮን ዳግም አስነስቶልናል።
በእነዚህ የዛፍ ጥላዎች ስር ሆነን፣ ከባቢ አየራችን እንዴት እንደተቀየረ መመስከር ጀምረናል። የተራቆቱ ተራሮቻችን አረንጓዴ ለብሰው የአፈር መሸርሸር ቆሟል፤ የጠፉ ምንጮቻችን ፈልቀው የተፈጥሮ የውሃ ዑደታችንን በሚገርም ሁኔታ መልሰነዋል።
ውይይታችን ወደ ኢኮኖሚያዊ ትሩፋቶቻችን ሄዶ፣ የተከልናቸው የፍራፍሬ እና የጥምር ደን ግብርና ችግኞች የምግብ ዋስትናችንን እያረጋገጡልን መሆኑን አንስተናል። ለወጣቶቻችን የስራ እድል ከመፍጠር ባለፈ፣ የቤተሰብ ገቢያችንን በከፍተኛ ደረጃ አሳድገንበታል።
ይህ አረንጓዴ ጉዞ ማህበራዊ ትስስራችንንም እጅግ አጠናክሮታል።
በክረምት ዝናብና ጭቃው ሳይበግረን አብረን የተከልነው እያንዳንዱ ችግኝ፣ የብሔራዊ አንድነታችንና የጋራ ራዕያችን ህያው ሀውልት ሆኖ ዛሬም በመካከላችን የፍቅር ጥላ ዘርግቷል።
እያደረግን ያለነው የአየር ንብረት ለውጥን የመከላከል ትግል ለዓለም ትልቅ ትምህርት ሆኗል። ከድርቅ ስጋት ተላቀን፣ ለምድራችን ጤንነት ግንባር ቀደም ጠበቆች በመሆናችን ልባዊ ኩራት ይሰማናል።
ከዛፎቹ ጥላ ስር የምንነሳው ለቀጣዩ ትውልድ የተሻለች እና የበለጸገች ሀገር ለማስረከብ ቃል በመግባት ነው። አረንጓዴ ዐሻራችን የህልውናችን መሰረት ሆኗል፡፡
2 days ago
“አሁን እየሠራን ያለነው ለልጆቻችን ነው“ - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
***************
በዛሬው ዕለት ኢትዮጵያ በአንድ ጀምበር የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር 800 ሚሊዮን ችግኞችን ለመትከል አቅዳ 805.3 ሚሊዮን ችግኞችን በመትከል ከዕቅዷ በላይ በማሳካት ድንቅ ውጤትን አስመዝግባለች።
ከማለዳው 12 ሰዓት ጀምሮ መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ በነቂስ ወጥትቶ እጁን ከአፈር ጋር አዋህዶ የነገዋን ኢትዮጵያ አረንጓዴ አልብሷል፡፡
ይህ የተባበረ ክንድ ኢትዮጵያ ተደምራ ስትነሳ ያቀደችውን የምትፈጽም፣ የማትለምንና ለተቸገሩ የምትደርስ በልጽጋ ሀገር መሆኗን ለአፍሪካም ሆነ ለዓለም በተግባር ያሳየ ነው፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአንድ ጀምበር 800 ሚሊዮን ችግኞችን የመትከል የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር ላይ ዐሻራቸው ባኖሩበት ወቅት፣ “አሁን እየሠራን ያለነው ለልጆቻችን ነው፤ ተስፋን ነው የምንተክለው፤ ነገን ነው የምንተክለው፤ ኢትዮጵያን ነው የምናለብሰው” የሚለውን ጥልቅ መልዕክት አስተላልፈዋል።
መልዕክታቸውም የችግኝ ተከላ ጥሪ ብቻ ሳይሆን፣ የኢትዮጵያ ነገን የመቅረጽ ታላቅ ሀገራዊ ራዕይ መግለጫ ነው። ይህ ኢትዮጵያ በምድር ላይ የምታሳርፈው አረንጓዴ መስመር ከዛሬ ባሻገር ለአያሌ ትውልዶች የሚሻገር ዘላቂ ሀብት መሆኑንም ያበስራል።
ዛሬ አፈር ውስጥ የምናስቀምጣት እያንዳንዷ ችግኝ ለነገው ትውልድ የምናስረክበው የሕይወት ዋስትና ናት። የአየር ንብረት ለውጥና የአፈር መሸርሸር በዓለም አቀፍ ደረጃ ስጋት በሆኑበት በዚህ ወቅት፣ ለልጆቻችን የሚበጅ የተፈጥሮ ሚዛኑ የተጠበቀ አካባቢን ማቆየት ትልቁ ቅርስ ነው።
ዛሬ በላባችን የምናጠጣት ችግኝ፣ ነገ ልጆቻችን ከስር ጥላዋ የሚጠለሉባት፣ ፍሬዋን የሚመገቡባት እና ንጹህ አየር የሚተነፍሱባት ደን ሆና ታድጋለች። ችግኝ መትከል የተፈጥሮ እንክብካቤ ብቻ ሳይሆን፣ የተስፋ አዋጅ ነው።
ዘርን በአፈር ውስጥ መቅበር ማለት ነገ እንደሚበቅል፣ እንደሚያድግና ፍሬ እንደሚያፈራ ማመን ነው። ሀገራችን በብዙ ፈተናዎች ውስጥ በሚታልፍበት ጊዜ አረንጓዴ ልምላሜን ማስፋፋት የሕዝቧን የተስፋ ስሜት የሚያድስ፣ የነገውን ብሩህ ጊዜ የሚያመላክት እና ተስፋ የመቁረጥን ድባብ በመስራት የሚያስወግድ ታላቅ መንፈሳዊ እና ማኅበራዊ እርምጃ ነው።
“ኢትዮጵያን ነው የምናለብሰው” የሚለው አገላለጽ ለአፈር መሬታችን የሚሰጠውን ክብር እና ውበት ያሳያል። የታረዙና የተራቆቱ ደጋዎችን፣ በጎርፍ የተጠረጉ ሜዳዎችን በአረንጓዴ አልባሳት ማሸበርቅ ሀገራዊ ግዴታችን ነው።
ሀገርን ማልበስ ድርቅን መከላከል፣ የውሃ ምንጮች እንዳይደርቁ ማድረግ እና የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ ነው። ኢትዮጵያ በደን ስትሸፈን ውበቷ ብቻ ሳይሆን ጥንካሬዋ እና ጽናቷም ይጎላል።
ዛሬ የምንተክለው ችግኝ የነገው ትውልድ የሚተነፍሰው አየር፣ የሚጠጣው ውሃ እና የሚጠለልበት ጥላ ነው፤ በመሆኑም የአረንጓዴ ዐሻራ የነገዋ ኢትዮጵያ መሠረት ነው።
የጠቅላይ ሚኒስትሩ መልዕክት እያንዳንዳችንን የሚያነቃ ነው። ችግኝ መትከል የቀን ተግባር ሳይሆን፣ የትውልድ አደራ መሆኑን ያስገነዝባል። በአንድ ጀምበር የተተከለው አረንጓዴ ዐሻራ፣ በኅብረት ከተነሳን ሀገራችንን ወደ ተሻለና ወደ ደመቀ ነገ መውሰድ እንደምንችል ማረጋገጫ ነው።
ዛሬ የምናፈስሰው እያንዳንዱ ላብ ነገ ለልጆቻችን የደስታና የልምላሜ ምንጭ ሆኖ ይመለሳል። በመሆኑም ይህን የተስፋ ጉዞ በእያንዳንድ መስክ አጠናክረን ማስቀጠል ይኖርብናል።
በአድማሱ አራጋው
***************
በዛሬው ዕለት ኢትዮጵያ በአንድ ጀምበር የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር 800 ሚሊዮን ችግኞችን ለመትከል አቅዳ 805.3 ሚሊዮን ችግኞችን በመትከል ከዕቅዷ በላይ በማሳካት ድንቅ ውጤትን አስመዝግባለች።
ከማለዳው 12 ሰዓት ጀምሮ መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ በነቂስ ወጥትቶ እጁን ከአፈር ጋር አዋህዶ የነገዋን ኢትዮጵያ አረንጓዴ አልብሷል፡፡
ይህ የተባበረ ክንድ ኢትዮጵያ ተደምራ ስትነሳ ያቀደችውን የምትፈጽም፣ የማትለምንና ለተቸገሩ የምትደርስ በልጽጋ ሀገር መሆኗን ለአፍሪካም ሆነ ለዓለም በተግባር ያሳየ ነው፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአንድ ጀምበር 800 ሚሊዮን ችግኞችን የመትከል የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር ላይ ዐሻራቸው ባኖሩበት ወቅት፣ “አሁን እየሠራን ያለነው ለልጆቻችን ነው፤ ተስፋን ነው የምንተክለው፤ ነገን ነው የምንተክለው፤ ኢትዮጵያን ነው የምናለብሰው” የሚለውን ጥልቅ መልዕክት አስተላልፈዋል።
መልዕክታቸውም የችግኝ ተከላ ጥሪ ብቻ ሳይሆን፣ የኢትዮጵያ ነገን የመቅረጽ ታላቅ ሀገራዊ ራዕይ መግለጫ ነው። ይህ ኢትዮጵያ በምድር ላይ የምታሳርፈው አረንጓዴ መስመር ከዛሬ ባሻገር ለአያሌ ትውልዶች የሚሻገር ዘላቂ ሀብት መሆኑንም ያበስራል።
ዛሬ አፈር ውስጥ የምናስቀምጣት እያንዳንዷ ችግኝ ለነገው ትውልድ የምናስረክበው የሕይወት ዋስትና ናት። የአየር ንብረት ለውጥና የአፈር መሸርሸር በዓለም አቀፍ ደረጃ ስጋት በሆኑበት በዚህ ወቅት፣ ለልጆቻችን የሚበጅ የተፈጥሮ ሚዛኑ የተጠበቀ አካባቢን ማቆየት ትልቁ ቅርስ ነው።
ዛሬ በላባችን የምናጠጣት ችግኝ፣ ነገ ልጆቻችን ከስር ጥላዋ የሚጠለሉባት፣ ፍሬዋን የሚመገቡባት እና ንጹህ አየር የሚተነፍሱባት ደን ሆና ታድጋለች። ችግኝ መትከል የተፈጥሮ እንክብካቤ ብቻ ሳይሆን፣ የተስፋ አዋጅ ነው።
ዘርን በአፈር ውስጥ መቅበር ማለት ነገ እንደሚበቅል፣ እንደሚያድግና ፍሬ እንደሚያፈራ ማመን ነው። ሀገራችን በብዙ ፈተናዎች ውስጥ በሚታልፍበት ጊዜ አረንጓዴ ልምላሜን ማስፋፋት የሕዝቧን የተስፋ ስሜት የሚያድስ፣ የነገውን ብሩህ ጊዜ የሚያመላክት እና ተስፋ የመቁረጥን ድባብ በመስራት የሚያስወግድ ታላቅ መንፈሳዊ እና ማኅበራዊ እርምጃ ነው።
“ኢትዮጵያን ነው የምናለብሰው” የሚለው አገላለጽ ለአፈር መሬታችን የሚሰጠውን ክብር እና ውበት ያሳያል። የታረዙና የተራቆቱ ደጋዎችን፣ በጎርፍ የተጠረጉ ሜዳዎችን በአረንጓዴ አልባሳት ማሸበርቅ ሀገራዊ ግዴታችን ነው።
ሀገርን ማልበስ ድርቅን መከላከል፣ የውሃ ምንጮች እንዳይደርቁ ማድረግ እና የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ ነው። ኢትዮጵያ በደን ስትሸፈን ውበቷ ብቻ ሳይሆን ጥንካሬዋ እና ጽናቷም ይጎላል።
ዛሬ የምንተክለው ችግኝ የነገው ትውልድ የሚተነፍሰው አየር፣ የሚጠጣው ውሃ እና የሚጠለልበት ጥላ ነው፤ በመሆኑም የአረንጓዴ ዐሻራ የነገዋ ኢትዮጵያ መሠረት ነው።
የጠቅላይ ሚኒስትሩ መልዕክት እያንዳንዳችንን የሚያነቃ ነው። ችግኝ መትከል የቀን ተግባር ሳይሆን፣ የትውልድ አደራ መሆኑን ያስገነዝባል። በአንድ ጀምበር የተተከለው አረንጓዴ ዐሻራ፣ በኅብረት ከተነሳን ሀገራችንን ወደ ተሻለና ወደ ደመቀ ነገ መውሰድ እንደምንችል ማረጋገጫ ነው።
ዛሬ የምናፈስሰው እያንዳንዱ ላብ ነገ ለልጆቻችን የደስታና የልምላሜ ምንጭ ሆኖ ይመለሳል። በመሆኑም ይህን የተስፋ ጉዞ በእያንዳንድ መስክ አጠናክረን ማስቀጠል ይኖርብናል።
በአድማሱ አራጋው
2 days ago
805.3 ሚሊዮን ችግኞች በአንድ ጀምበር፤ የኢትዮጵያውያን ተአምራዊ ውሎ
*********************
ዛሬ በመላው ኢትዮጵያ “ተስፋን እንትከል” በሚል መሪ ቃል በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎች በአንድ ልብ እና በአንድ መንፈስ በመንቀሳቀስ በአንድ ጀምበር 805.3 ሚሊዮን ችግኞችን በመትከል አዲስ ታሪክ ፅፈዋል።
ኢትዮጵያውያን የዕድሜ ልዩነት ሳይበግራቸው ከሕፃናት እስከ አዛውንት ከአካል ጉዳተኞች እስከ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ሃላፊዎች በጋራ በመሆን አረንጓዴ አሻራቸውን አሳርፈዋል። ይህ የነቃ ተሳትፎም የማህበረሰቡን አንድነትና ለአካባቢ ጥበቃ ያላቸውን ጽኑ ቁርጠኝነት በግልጽ ያሳየ ነው።
ይህ መርሃ ግብር ልጆችን በማሳተፍ ስለ አካባቢ ጥበቃ አስፈላጊነት በተግባር የሚማሩበት ልዩ መድረክ ሆኗል። ህፃናት ከወዲሁ የችግኝ እንክብካቤን እንደ ባህል እንዲለምዱና የነገዋን አረንጓዴ አገር የመረከብ ሃላፊነታቸውን ገና በሕፃንነታቸው እንዲረዱ ያግዛል።
በተጨማሪም ሀገራዊ አንድነትን በተግባር ከመግለጹ በላይ ለአየር ንብረት ለውጥ አሳሳቢ ፈተናዎች ምላሽ ለመስጠትና የኢትዮጵያን የመጻኢ ዘመን ዕጣ ፈንታ በጽኑ መሠረት ላይ ለመገንባት ያለመ ንቅናቄ ነው።
ይህ የተቀናጀ ሀገራዊ ርብርብ የትናንቱ የአድዋ ድል የነፃነት አርበኝነት በተፈጥሮ ጥበቃ የሚደገምበት የዘመናችን የጀግንነት ምዕራፍ ተደርጎ ይወሰዳል።
ቀደምት አባቶች በአድዋ ተራሮች ላይ ልዩነቶቻቸውን አክስመው ለሀገር ነፃነት እንደቆሙ ሁሉ የዛሬው ትውልድም ድህነትንና የተፈጥሮ መራቆትን ለማሸነፍ ዕውቀቱን ጉልበቱንና ፍቅሩን አስተባብሮ ኢትዮጵያን አረንጓዴ የማልበስ ኃላፊነቱን እየተወጣ ይገኛል።
የምትተከለው እያንዳንዷ ችግኝ የተራቆቱ መሬቶች መልሰው እንዲያገግሙ የአፈር መሸርሸርና የጎርፍ አደጋዎች እንዲቀንሱ እንዲሁም የከርሰ ምድር ውሃ እንዲበለጽግ በማድረግ ረገድ ትልቁን ድርሻ ታበረክታለች።
ከአካባቢ ጥበቃ ፋይዳው ባሻገር መርሐ ግብሩ የሀገሪቱን ምጣኔ ሀብት የሚያነቃቃ ታላቅ ዕድል ፈጥሯል። በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ወጣቶች በችግኝ ማፍላት በጉድጓድ ዝግጅትና በተከላ ሥራዎች በመሰማራት ሰፊ የሥራ ዕድል ያገኙ ሲሆን በተለይም እንደ ቡና፣ አቮካዶና ማንጎ ያሉ የኢኮኖሚ ጠቀሜታ ያላቸው ተክሎች ትኩረት ማግኘታቸው ለአርሶ አደሩ ተጨማሪ የገቢ ምንጭ በመሆን የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ መሠረት ጥሏል።
በተጨማሪም ይህ ሀገራዊ ጥረት በዓለም አቀፍ ደረጃ የአየር ንብረት መዛባትን ለመቋቋም የሚረዳና ኢትዮጵያ ለዓለም አረንጓዴ ልማት ያላትን ቁርጠኝነት የሚያሳይ ሕያው ውርስ ነው።
ይህ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በቅድመ ዝግጅት ከተያዘው እቅድ በላይ በመፈጸም በዛሬዉ ዕለት ብቻ 805.3 ሚሊዮን ችግኞች የተተከሉ ሲሆን 26.2 ሚሊየን ሰዎች ተሳትፈዋል በዚህም 291.4 ሺህ ሄክታር መሬት መሸፈን ተችሏል በዚህም ታሪካዊ ስኬት ተመዝግቧል።
ይህ በዓይነቱ ልዩ የሆነው አገራዊ የችግኝ ተከላ ዘመቻ የህዝባችንን የተቀናጀ የተቀናጀ ጥረት እና ለአካባቢ ጥበቃ ያለውን ቁርጠኝነት በአለም አቀፍ ደረጃ ታላቅ ሁነት ሆኖ አልፏል።
በዘንድሮው አመት እስካሁን ባለው ጊዜ ከ6.5 ቢሊዮን በላይ ችግኞች መተከላቸው የተገለጸ ሲሆን የተያዘውን አጠቃላይ እቅድ ለማጠናቀቅ ቀሪ የሆኑት 1.5 ቢሊዮን ችግኞች ደግሞ በሚቀጥሉት ወራት ተተክለው የሚጠናቀቁ ይሆናል።
የዚህ ታሪካዊ ዘመቻ እውነተኛ ስኬት የሚለካው በተከላው ሂደት ብቻ ሳይሆን ከተከላ በኋላ በሚደረግ ቀጣይነት ያለው እንክብካቤና ጥበቃ በመሆኑ እያንዳንዱ ዜጋ የተከላቸውን ችግኞች ተንከባክቦ ለፍሬ የማብቃት አደራ አለበት።
በብሌን ደምበሎ
*********************
ዛሬ በመላው ኢትዮጵያ “ተስፋን እንትከል” በሚል መሪ ቃል በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎች በአንድ ልብ እና በአንድ መንፈስ በመንቀሳቀስ በአንድ ጀምበር 805.3 ሚሊዮን ችግኞችን በመትከል አዲስ ታሪክ ፅፈዋል።
ኢትዮጵያውያን የዕድሜ ልዩነት ሳይበግራቸው ከሕፃናት እስከ አዛውንት ከአካል ጉዳተኞች እስከ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ሃላፊዎች በጋራ በመሆን አረንጓዴ አሻራቸውን አሳርፈዋል። ይህ የነቃ ተሳትፎም የማህበረሰቡን አንድነትና ለአካባቢ ጥበቃ ያላቸውን ጽኑ ቁርጠኝነት በግልጽ ያሳየ ነው።
ይህ መርሃ ግብር ልጆችን በማሳተፍ ስለ አካባቢ ጥበቃ አስፈላጊነት በተግባር የሚማሩበት ልዩ መድረክ ሆኗል። ህፃናት ከወዲሁ የችግኝ እንክብካቤን እንደ ባህል እንዲለምዱና የነገዋን አረንጓዴ አገር የመረከብ ሃላፊነታቸውን ገና በሕፃንነታቸው እንዲረዱ ያግዛል።
በተጨማሪም ሀገራዊ አንድነትን በተግባር ከመግለጹ በላይ ለአየር ንብረት ለውጥ አሳሳቢ ፈተናዎች ምላሽ ለመስጠትና የኢትዮጵያን የመጻኢ ዘመን ዕጣ ፈንታ በጽኑ መሠረት ላይ ለመገንባት ያለመ ንቅናቄ ነው።
ይህ የተቀናጀ ሀገራዊ ርብርብ የትናንቱ የአድዋ ድል የነፃነት አርበኝነት በተፈጥሮ ጥበቃ የሚደገምበት የዘመናችን የጀግንነት ምዕራፍ ተደርጎ ይወሰዳል።
ቀደምት አባቶች በአድዋ ተራሮች ላይ ልዩነቶቻቸውን አክስመው ለሀገር ነፃነት እንደቆሙ ሁሉ የዛሬው ትውልድም ድህነትንና የተፈጥሮ መራቆትን ለማሸነፍ ዕውቀቱን ጉልበቱንና ፍቅሩን አስተባብሮ ኢትዮጵያን አረንጓዴ የማልበስ ኃላፊነቱን እየተወጣ ይገኛል።
የምትተከለው እያንዳንዷ ችግኝ የተራቆቱ መሬቶች መልሰው እንዲያገግሙ የአፈር መሸርሸርና የጎርፍ አደጋዎች እንዲቀንሱ እንዲሁም የከርሰ ምድር ውሃ እንዲበለጽግ በማድረግ ረገድ ትልቁን ድርሻ ታበረክታለች።
ከአካባቢ ጥበቃ ፋይዳው ባሻገር መርሐ ግብሩ የሀገሪቱን ምጣኔ ሀብት የሚያነቃቃ ታላቅ ዕድል ፈጥሯል። በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ወጣቶች በችግኝ ማፍላት በጉድጓድ ዝግጅትና በተከላ ሥራዎች በመሰማራት ሰፊ የሥራ ዕድል ያገኙ ሲሆን በተለይም እንደ ቡና፣ አቮካዶና ማንጎ ያሉ የኢኮኖሚ ጠቀሜታ ያላቸው ተክሎች ትኩረት ማግኘታቸው ለአርሶ አደሩ ተጨማሪ የገቢ ምንጭ በመሆን የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ መሠረት ጥሏል።
በተጨማሪም ይህ ሀገራዊ ጥረት በዓለም አቀፍ ደረጃ የአየር ንብረት መዛባትን ለመቋቋም የሚረዳና ኢትዮጵያ ለዓለም አረንጓዴ ልማት ያላትን ቁርጠኝነት የሚያሳይ ሕያው ውርስ ነው።
ይህ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በቅድመ ዝግጅት ከተያዘው እቅድ በላይ በመፈጸም በዛሬዉ ዕለት ብቻ 805.3 ሚሊዮን ችግኞች የተተከሉ ሲሆን 26.2 ሚሊየን ሰዎች ተሳትፈዋል በዚህም 291.4 ሺህ ሄክታር መሬት መሸፈን ተችሏል በዚህም ታሪካዊ ስኬት ተመዝግቧል።
ይህ በዓይነቱ ልዩ የሆነው አገራዊ የችግኝ ተከላ ዘመቻ የህዝባችንን የተቀናጀ የተቀናጀ ጥረት እና ለአካባቢ ጥበቃ ያለውን ቁርጠኝነት በአለም አቀፍ ደረጃ ታላቅ ሁነት ሆኖ አልፏል።
በዘንድሮው አመት እስካሁን ባለው ጊዜ ከ6.5 ቢሊዮን በላይ ችግኞች መተከላቸው የተገለጸ ሲሆን የተያዘውን አጠቃላይ እቅድ ለማጠናቀቅ ቀሪ የሆኑት 1.5 ቢሊዮን ችግኞች ደግሞ በሚቀጥሉት ወራት ተተክለው የሚጠናቀቁ ይሆናል።
የዚህ ታሪካዊ ዘመቻ እውነተኛ ስኬት የሚለካው በተከላው ሂደት ብቻ ሳይሆን ከተከላ በኋላ በሚደረግ ቀጣይነት ያለው እንክብካቤና ጥበቃ በመሆኑ እያንዳንዱ ዜጋ የተከላቸውን ችግኞች ተንከባክቦ ለፍሬ የማብቃት አደራ አለበት።
በብሌን ደምበሎ
Sponsored by
Surafel
2 days ago
የጤናው ዘርፍ የአረንጓዴ አሻራ ተሳትፎ
📌 ከ30 ሺህ በላይ ችግኞች በዛሬው እለት ተተክለዋል
#ethiopia | በሀገር አቀፍ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር ላይ የጤና ሚኒስቴር እና የተጠሪ ተቋማት አመራሮች እንዲሁም ሰራተኞች ከኢትዮጵያ የአካል ድጋፍ አገልግሎት ከገፈርሳ ጉጄ ክፍለ ከተማ ጋር በመተባበር በዛሬ እለት በገፈርሳ ሰው ሰራሽ ሀይቅ ዳርቻ ከ30 ሺህ በላይ ችግኞች በዛሬው እለት ተተክለዋል።
በሸገር ከተማ በገፈርሳ ጉጄ አካባቢ በተካሄደው በዚህ የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር ላይ የጤና ሚኒስትሯ ክብርት ዶክተር መቅደስ ዳባ፣ ሚኒስትር ዴኤታዎች እና የየደረጃው የአካባቢው አመራሮች እንዲሁም የሀገር መከላከያ ሰራዊት አባላትና የማህበረሰብ ክፍሎች ከማለዳው 1 ሰዓት ጀምሮ በመገኘት ችግኝ ተክለዋል።
የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ደረጄ ዱጉማ በዚሁ ወቅት ባደረጉት ንግግር፣ አረንጓዴ አሻራ እና የጤና ዘርፍ የማይለያዩ የአንድ ሳንቲም ሁለት ገጽታዎች መሆናቸውን ገልጸዋል። ችግኝ ለአካባቢ ጥበቃ ብቻ ሳይሆን ለህብረተሰብ ጤና፣ ለንጹህ አየር እና ለምግብ ዋስትና ማሻሻያ ወሳኝ ሚና እንደሚጫወት የጠቆሙት ሚኒስትር ዴኤታው፣ በተለይም ለአዲስ አበባ እና ለአካባቢው ህዝብ የንጹህ ውሃ ምንጭ የሆነውን የገፈርሳ አካባቢን መንከባከብ የሁላችንም ህብረ-ብሄራዊ ሀገራዊ ኃላፊነት እንደሆነ አስገንዝበዋል።
በዕለቱ በቦታው ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የጤና ሚኒስትሯ ክብርት ዶክተር መቅደስ ዳባ በበኩላቸው፣ ኢትዮጵያ የተፈጥሮ አካባቢዋን ለመጠበቅ የምታደርገው ጥረት በንግግር ሳይሆን በተግባር የሚገለጽ መሆኑን አብራርተዋል።
በዕለቱ ሚኒስቴሩ ከተጠሪ ተቋማት ጋር በመሆን ከ30 ሺህ በላይ ችግኞችን የተከለ ሲሆን፣ በክረምቱ የክረምት በጎ ፈቃድ መርሃ-ግብር ደግሞ በሀገር አቀፍ ደረጃ እስከ 250 ሺህ ችግኞችን ለመትከል እና ከ20 ሚሊዮን በላይ ዜጎችን ነጻ የህክምና አገልግሎት ለመስጠት ታቅዶ እየተሰራ እንደሚገኝ ሚኒስትሯ ገልጸዋል።
በመጨረሻም ክብርት ሚኒስትሯ፣ የጤና ባለሙያዎች እና መላው የሀገራችን ህዝብ ቀኑ ሳያልቅ እና ጀምበር ሳትጠልቅ የድርሻቸውን ችግኝ በመትከል የዚህ ታሪካዊ ኩነት አካል እንዲሆኑ ጥሪ አቅርበዋል።
ከችግኝ ተከላው መርሐግብር ባሻገር የኢትዮጵያ የአካል ድጋፍ አገልግሎት በሸገር ከተማ ከ200 በላይ ለሚሆኑ ተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ ተደርጓል።
በጌትነት ተመስገን
📷 ከበደ መክብብ
#ministryofhealth #treeplanting
#climateaction #publichealth
#environmentalhealth #gefersa #cleanenvironment #greenethiopia
#communitysupport
📌 ከ30 ሺህ በላይ ችግኞች በዛሬው እለት ተተክለዋል
#ethiopia | በሀገር አቀፍ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር ላይ የጤና ሚኒስቴር እና የተጠሪ ተቋማት አመራሮች እንዲሁም ሰራተኞች ከኢትዮጵያ የአካል ድጋፍ አገልግሎት ከገፈርሳ ጉጄ ክፍለ ከተማ ጋር በመተባበር በዛሬ እለት በገፈርሳ ሰው ሰራሽ ሀይቅ ዳርቻ ከ30 ሺህ በላይ ችግኞች በዛሬው እለት ተተክለዋል።
በሸገር ከተማ በገፈርሳ ጉጄ አካባቢ በተካሄደው በዚህ የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር ላይ የጤና ሚኒስትሯ ክብርት ዶክተር መቅደስ ዳባ፣ ሚኒስትር ዴኤታዎች እና የየደረጃው የአካባቢው አመራሮች እንዲሁም የሀገር መከላከያ ሰራዊት አባላትና የማህበረሰብ ክፍሎች ከማለዳው 1 ሰዓት ጀምሮ በመገኘት ችግኝ ተክለዋል።
የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ደረጄ ዱጉማ በዚሁ ወቅት ባደረጉት ንግግር፣ አረንጓዴ አሻራ እና የጤና ዘርፍ የማይለያዩ የአንድ ሳንቲም ሁለት ገጽታዎች መሆናቸውን ገልጸዋል። ችግኝ ለአካባቢ ጥበቃ ብቻ ሳይሆን ለህብረተሰብ ጤና፣ ለንጹህ አየር እና ለምግብ ዋስትና ማሻሻያ ወሳኝ ሚና እንደሚጫወት የጠቆሙት ሚኒስትር ዴኤታው፣ በተለይም ለአዲስ አበባ እና ለአካባቢው ህዝብ የንጹህ ውሃ ምንጭ የሆነውን የገፈርሳ አካባቢን መንከባከብ የሁላችንም ህብረ-ብሄራዊ ሀገራዊ ኃላፊነት እንደሆነ አስገንዝበዋል።
በዕለቱ በቦታው ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የጤና ሚኒስትሯ ክብርት ዶክተር መቅደስ ዳባ በበኩላቸው፣ ኢትዮጵያ የተፈጥሮ አካባቢዋን ለመጠበቅ የምታደርገው ጥረት በንግግር ሳይሆን በተግባር የሚገለጽ መሆኑን አብራርተዋል።
በዕለቱ ሚኒስቴሩ ከተጠሪ ተቋማት ጋር በመሆን ከ30 ሺህ በላይ ችግኞችን የተከለ ሲሆን፣ በክረምቱ የክረምት በጎ ፈቃድ መርሃ-ግብር ደግሞ በሀገር አቀፍ ደረጃ እስከ 250 ሺህ ችግኞችን ለመትከል እና ከ20 ሚሊዮን በላይ ዜጎችን ነጻ የህክምና አገልግሎት ለመስጠት ታቅዶ እየተሰራ እንደሚገኝ ሚኒስትሯ ገልጸዋል።
በመጨረሻም ክብርት ሚኒስትሯ፣ የጤና ባለሙያዎች እና መላው የሀገራችን ህዝብ ቀኑ ሳያልቅ እና ጀምበር ሳትጠልቅ የድርሻቸውን ችግኝ በመትከል የዚህ ታሪካዊ ኩነት አካል እንዲሆኑ ጥሪ አቅርበዋል።
ከችግኝ ተከላው መርሐግብር ባሻገር የኢትዮጵያ የአካል ድጋፍ አገልግሎት በሸገር ከተማ ከ200 በላይ ለሚሆኑ ተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ ተደርጓል።
በጌትነት ተመስገን
📷 ከበደ መክብብ
#ministryofhealth #treeplanting
#climateaction #publichealth
#environmentalhealth #gefersa #cleanenvironment #greenethiopia
#communitysupport
2 days ago
በጅማ ዞን «ተስፋን እንትከል» በሚል መርህ የአንድ ጀምበር ችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ተካሄደ
#fastmereja I በኦሮሚያ ክልል ጅማ ዞን፣ ሰቃ ወረዳ ቡዬ ቀጨማ ቀበሌ ዛሬ ሐምሌ 27 ቀን 2018 ዓ.ም «ተስፋን እንትከል» በሚል መርህ የመላው ኢትዮጵያውያንን ጥሪ ያቀናጀ ታላቅ የአንድ ጀምበር የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር በተሳካ ሁኔታ ተከናውኗል። ይህ በአገር አቀፍ ደረጃ በአንድ ጀምበር ከ800 ሚሊዮን በላይ ችግኞችን ለመትከል በተያዘው አገራዊ ግብ መሠረት የተከናወነ ሲሆን፣ የአረንጓዴ አሻራን በማሳረፍ ረገድ የትውልድ ሀላፊነትን ለመወጣት ያለመ አገራዊ ጥረት አካል እንደሆነ ተገልጿል።
ይህ ሀገር አቀፍ አቅጣጫን መሠረት ያደረገ ታላቅ መርሃ ግብር በግሪን ዌቭ አሊያንስ ሀገር በቀል ግብረ-ሰናይ ድርጅት፣ ከኢፌድሪ ግብርና ሚኒስቴር እና ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጋር በመተባበር የተዘጋጀ ነው። በተጨማሪም የኢትዮጵያ አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን እና የኦሮሚያ ግብርና ቢሮ አስፈላጊውን የቴክኒክ ድጋፍ በማድረግ ለዝግጅቱ ስኬት ከፍተኛ አስተዋጽኦ አበርክተዋል።
በዕለቱ በተካሄደው የችግኝ ተከላ ስነ-ስርዓት ላይ የመንግሥት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶችን ጨምሮ በርካታ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል። ከታደሙት የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች መካከል የግብርና ሚኒስቴር ደኤታ ዶክተር ኢፋ ሙለታ፣ የጅማ ዞን አስተዳዳሪ አቶ ቲጃኒ ናስር፣ የባህል እና ስፖርት ሚኒስቴር ደኤታ ነፊሳ አልመሃዲ፣ የግሪን ዌቭ አሊያንስ መስራች አምባሳደር ሚካኤል ነጋሳ እንዲሁም የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ መልካሙ ዴሲሳ ይገኙበታል።
በተጨማሪም የአካባቢው ነዋሪዎች፣ ታዋቂ ግለሰቦች፣ አርቲስቶች፣ ጋዜጠኞች እና የቲክቶክ ይዘት ፈጣሪዎች በስፍራው በመገኘት አረንጓዴ አሻራቸውን በማሳረፍ ንቁ ተሳትፎ አድርገዋል።
መርሃ ግብሩ የተፈጥሮ ሀብት እንክብካቤን ለማጠናከር እና የወደፊት ትውልድን የወደፊት እጣ ፈንታ በተግባር ለመገንባት ያለመ መሆኑን አዘጋጆቹ አስታውቀዋል።
#fastmereja I በኦሮሚያ ክልል ጅማ ዞን፣ ሰቃ ወረዳ ቡዬ ቀጨማ ቀበሌ ዛሬ ሐምሌ 27 ቀን 2018 ዓ.ም «ተስፋን እንትከል» በሚል መርህ የመላው ኢትዮጵያውያንን ጥሪ ያቀናጀ ታላቅ የአንድ ጀምበር የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር በተሳካ ሁኔታ ተከናውኗል። ይህ በአገር አቀፍ ደረጃ በአንድ ጀምበር ከ800 ሚሊዮን በላይ ችግኞችን ለመትከል በተያዘው አገራዊ ግብ መሠረት የተከናወነ ሲሆን፣ የአረንጓዴ አሻራን በማሳረፍ ረገድ የትውልድ ሀላፊነትን ለመወጣት ያለመ አገራዊ ጥረት አካል እንደሆነ ተገልጿል።
ይህ ሀገር አቀፍ አቅጣጫን መሠረት ያደረገ ታላቅ መርሃ ግብር በግሪን ዌቭ አሊያንስ ሀገር በቀል ግብረ-ሰናይ ድርጅት፣ ከኢፌድሪ ግብርና ሚኒስቴር እና ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጋር በመተባበር የተዘጋጀ ነው። በተጨማሪም የኢትዮጵያ አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን እና የኦሮሚያ ግብርና ቢሮ አስፈላጊውን የቴክኒክ ድጋፍ በማድረግ ለዝግጅቱ ስኬት ከፍተኛ አስተዋጽኦ አበርክተዋል።
በዕለቱ በተካሄደው የችግኝ ተከላ ስነ-ስርዓት ላይ የመንግሥት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶችን ጨምሮ በርካታ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል። ከታደሙት የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች መካከል የግብርና ሚኒስቴር ደኤታ ዶክተር ኢፋ ሙለታ፣ የጅማ ዞን አስተዳዳሪ አቶ ቲጃኒ ናስር፣ የባህል እና ስፖርት ሚኒስቴር ደኤታ ነፊሳ አልመሃዲ፣ የግሪን ዌቭ አሊያንስ መስራች አምባሳደር ሚካኤል ነጋሳ እንዲሁም የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ መልካሙ ዴሲሳ ይገኙበታል።
በተጨማሪም የአካባቢው ነዋሪዎች፣ ታዋቂ ግለሰቦች፣ አርቲስቶች፣ ጋዜጠኞች እና የቲክቶክ ይዘት ፈጣሪዎች በስፍራው በመገኘት አረንጓዴ አሻራቸውን በማሳረፍ ንቁ ተሳትፎ አድርገዋል።
መርሃ ግብሩ የተፈጥሮ ሀብት እንክብካቤን ለማጠናከር እና የወደፊት ትውልድን የወደፊት እጣ ፈንታ በተግባር ለመገንባት ያለመ መሆኑን አዘጋጆቹ አስታውቀዋል።
2 days ago
#ethiopia | "ኢትዮጵያውያን ዝቅ ብለው ለመሬት አደራ ይሰጣሉ፤ ምድርም የተሰጣትን አደራ እጥፍ አድርጋ ትመልሳለች፡፡"
- የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር
እናት አለም መለሰ
***
በአንድ ጀምበር 800 ሚሊዮን ችግኞችን ለመትከል የተዘጋጀው ታሪካዊ ሀገራዊ መርሐ ግብር በይፋ ተጀመረ
ኢትዮጵያ በአንድ ቀን 800 ሚሊዮን ችግኞችን በመትከል አዲስ ታሪክ ለመጻፍ ያቀደችውን ሀገራዊ የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር ዛሬ በይፋ ጀምራለች።
የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር እናትዓለም መለሰ በሰጡት መግለጫ፣ መላው ኢትዮጵያውያን የተጎሳቀለችውን ምድር ለመመለስና ለቀጣይ ትውልድ ዘላቂ አሻራ ለማኖር በአንድነት መነሳታቸውን ገልጸዋል።
ሚኒስትሯ፣ “ኢትዮጵያውያን ዝቅ ብለው ለምድር አደራ ይሰጣሉ፤ ምድርም የተሰጣትን አደራ እጥፍ አድርጋ ትመልሳለች” በማለት የሕዝቡን የአንድነት መንፈስና ለተፈጥሮ ያለውን ቁርጠኝነት አድንቀዋል።
በ“ኑ ተስፋን እንትከል” በሚል መሪ ሐሳብ የሚካሄደው የዘንድሮው ዘመቻ፣ በመደመር መርህ ሁሉም የማኅበረሰብ ክፍሎች በንቃት እንዲሳተፉና 800 ሚሊዮን ችግኞችን በአንድ ቀን የመትከል ግብ እንዲሳካ ጥሪ ቀርቧል።
መርሐ ግብሩ ዛሬ ሐምሌ 27/2018 ዓ.ም. እስከ ምሽቱ 12 ሰዓት ድረስ በመላው ኢትዮጵያ በሚገኙ ሁሉም ክልሎችና የማኅበረሰብ ክፍሎች ተሳትፎ በሰፊው እንደሚከናወን ተገልጿል።
ይህ የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር በአካባቢ ጥበቃ፣ የደን ሽፋን መጨመር፣ የአየር ንብረት ለውጥን መቋቋም እና ለቀጣዩ ትውልድ አረንጓዴ ኢትዮጵያን ለማስረከብ ከሚደረጉ ሀገራዊ ጥረቶች መካከል ቁልፍ ተነሳሽነት መሆኑ ተጠቅሷል።
#አረንጓዴአሻራ #greenlegacy #ethiopia #planttrees #climateaction #ጌጡተመስገን #getutemesgen
- የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር
እናት አለም መለሰ
***
በአንድ ጀምበር 800 ሚሊዮን ችግኞችን ለመትከል የተዘጋጀው ታሪካዊ ሀገራዊ መርሐ ግብር በይፋ ተጀመረ
ኢትዮጵያ በአንድ ቀን 800 ሚሊዮን ችግኞችን በመትከል አዲስ ታሪክ ለመጻፍ ያቀደችውን ሀገራዊ የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር ዛሬ በይፋ ጀምራለች።
የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር እናትዓለም መለሰ በሰጡት መግለጫ፣ መላው ኢትዮጵያውያን የተጎሳቀለችውን ምድር ለመመለስና ለቀጣይ ትውልድ ዘላቂ አሻራ ለማኖር በአንድነት መነሳታቸውን ገልጸዋል።
ሚኒስትሯ፣ “ኢትዮጵያውያን ዝቅ ብለው ለምድር አደራ ይሰጣሉ፤ ምድርም የተሰጣትን አደራ እጥፍ አድርጋ ትመልሳለች” በማለት የሕዝቡን የአንድነት መንፈስና ለተፈጥሮ ያለውን ቁርጠኝነት አድንቀዋል።
በ“ኑ ተስፋን እንትከል” በሚል መሪ ሐሳብ የሚካሄደው የዘንድሮው ዘመቻ፣ በመደመር መርህ ሁሉም የማኅበረሰብ ክፍሎች በንቃት እንዲሳተፉና 800 ሚሊዮን ችግኞችን በአንድ ቀን የመትከል ግብ እንዲሳካ ጥሪ ቀርቧል።
መርሐ ግብሩ ዛሬ ሐምሌ 27/2018 ዓ.ም. እስከ ምሽቱ 12 ሰዓት ድረስ በመላው ኢትዮጵያ በሚገኙ ሁሉም ክልሎችና የማኅበረሰብ ክፍሎች ተሳትፎ በሰፊው እንደሚከናወን ተገልጿል።
ይህ የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር በአካባቢ ጥበቃ፣ የደን ሽፋን መጨመር፣ የአየር ንብረት ለውጥን መቋቋም እና ለቀጣዩ ትውልድ አረንጓዴ ኢትዮጵያን ለማስረከብ ከሚደረጉ ሀገራዊ ጥረቶች መካከል ቁልፍ ተነሳሽነት መሆኑ ተጠቅሷል።
#አረንጓዴአሻራ #greenlegacy #ethiopia #planttrees #climateaction #ጌጡተመስገን #getutemesgen
3 days ago
ለትውልድ የሚሻገር አኩሪ ታሪክ የሚጻፍበት የአንድ ጀንበር ችግኝ ተከላ
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 26፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ኢትዮጵያ ከ2011 ዓ.ም ጀምሮ በአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር አማካኝነት የደን ሀብቷን ለማሳደግ፣ የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖዎችን የመቋቋም ጉዞ ዛሬ ላይ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚጠቀስ አርአያነት ያለው ተግባር ሆኗል።
ይህ በየዓመቱ በከፍተኛ ህዝባዊ ንቅናቄ የሚታወቀው መርሐ ግብር የተፈጥሮ ሚዛንን በመጠበቅ የወደፊት ትውልድ ተስፋን በጽኑ መሠረት ላይ የሚያንጽ ብሔራዊ ንቅናቄ ነው።
በየዓመቱ የሚካሄደው የአንድ ጀንበር የችግኝ ተከላ መርሐ ግብር ሚሊየኖች ከዳር እስከ ዳር በዝናብና በብርድ ሳይበገሩ በመዝመት ምድርን የሚያለመልሙበት መድረክ ሆኗል።
ነገ ማለዳ በይፋ ለሚጀመረው የዘንድሮው የአንድ ጀንበር የችግኝ ተከላ መርሐ ግብር እንደ ሀገር አስፈላጊው ዝግጅት ተደርጓል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ባስተላለፉት መልዕክት፥ የነገው መርሐ ግብር የኢትዮጵያውያን ክንድ ተባብሮ፣ በአንድ ጀንበር 800 ሚሊየን ችግኞችን በመትከል ሌላ ታሪክ የምንሰራበት ነው ብለዋል፡፡
የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር የደን ሽፋንን በእጥፍ ከማሳደግ ባሻገር፣ የአፈር መሸርሸርን ለመከላከል፣ የውሃ አካላትን ለማበልጸግና የግብርና ምርታማነትን በዘላቂነት ለማሳደግ የጎላ ሚና ይጫወታል።
ከዚሁ ጎን ለጎን የሚተከሉት ችግኞች የምግብ ዋስትናን የሚያረጋግጡ የፍራፍሬ ተክሎች እንዲሁም የኢኮኖሚ ጥቅም የሚሰጡ የዛፍ ዝርያዎችን ያካተቱ በመሆናቸው ለሀገራችን የኢኮኖሚ እድገት አዎንታዊ አስተዋጽኦ ያበረክታሉ።
ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የችግኝ ተከላ ዘመቻዎች ሕዝቡ ባደረገው ከፍተኛ ተሳትፎ መርሐ ግብሩ ከአካባቢ ጥበቃ ባለፈ የሀገራዊ አንድነት መገለጫ መሆን ችሏል።
800 ሚሊየን ችግኞችን በአንድ ጀንበር የመትከል ዘመቻው ለኢትዮጵያ የአረንጓዴ ልማት፣ የአየር ንብረት ተጽዕኖን ለመቋቋም፣ ለምግብ ዋስትናና ለትውልድ ተሻጋሪ የተፈጥሮ ሀብት ግንባታ የሚያበረክተውን ድርሻ የበለጠ የሚያጎላ ነው።
እያንዳንዱ ዜጋ ከጫፍ እስከ ጫፍ በመነሳት የድርሻውን እንዲወጣ የሚጠይቀው ይህ ሀገራዊ ጥሪ በከተማም ሆነ በገጠር የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን በማለዳው በመውጣት የራሳቸውን ታሪካዊ ዐሻራ እንዲያኖሩ በር የከፈተ ሆኗል።
ይህ እቅድ የቁጥር ጉዳይ ብቻ ሳይሆን የጽናት፣ የህብረትና የልማት ታላቅ መገለጫ በመሆኑ ኢትዮጵያውያን በተፈጥሮ ሀብታቸው ላይ አዲስ ሕይወት የሚዘሩበት፣ ለቀጣዩ ትውልድ ለም እና አረንጓዴ ሀገር የሚያስረክቡበት ታሪካዊ አጋጣሚ ነው።
ችግኞችን ከመትከል ባለፈ የመንከባከብና የመጠበቅ ባሕልን ማሳደግ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር ዋነኛ ምሰሶ በመሆኑ እያንዳንዱ የተተከለ ችግኝ ጸድቆ ለፍሬ እንዲበቃ ሁሉም አካላት የተቀናጀ ጥረትና ክትትል ማድረግ ይጠበቅባቸዋል።
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 26፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ኢትዮጵያ ከ2011 ዓ.ም ጀምሮ በአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር አማካኝነት የደን ሀብቷን ለማሳደግ፣ የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖዎችን የመቋቋም ጉዞ ዛሬ ላይ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚጠቀስ አርአያነት ያለው ተግባር ሆኗል።
ይህ በየዓመቱ በከፍተኛ ህዝባዊ ንቅናቄ የሚታወቀው መርሐ ግብር የተፈጥሮ ሚዛንን በመጠበቅ የወደፊት ትውልድ ተስፋን በጽኑ መሠረት ላይ የሚያንጽ ብሔራዊ ንቅናቄ ነው።
በየዓመቱ የሚካሄደው የአንድ ጀንበር የችግኝ ተከላ መርሐ ግብር ሚሊየኖች ከዳር እስከ ዳር በዝናብና በብርድ ሳይበገሩ በመዝመት ምድርን የሚያለመልሙበት መድረክ ሆኗል።
ነገ ማለዳ በይፋ ለሚጀመረው የዘንድሮው የአንድ ጀንበር የችግኝ ተከላ መርሐ ግብር እንደ ሀገር አስፈላጊው ዝግጅት ተደርጓል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ባስተላለፉት መልዕክት፥ የነገው መርሐ ግብር የኢትዮጵያውያን ክንድ ተባብሮ፣ በአንድ ጀንበር 800 ሚሊየን ችግኞችን በመትከል ሌላ ታሪክ የምንሰራበት ነው ብለዋል፡፡
የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር የደን ሽፋንን በእጥፍ ከማሳደግ ባሻገር፣ የአፈር መሸርሸርን ለመከላከል፣ የውሃ አካላትን ለማበልጸግና የግብርና ምርታማነትን በዘላቂነት ለማሳደግ የጎላ ሚና ይጫወታል።
ከዚሁ ጎን ለጎን የሚተከሉት ችግኞች የምግብ ዋስትናን የሚያረጋግጡ የፍራፍሬ ተክሎች እንዲሁም የኢኮኖሚ ጥቅም የሚሰጡ የዛፍ ዝርያዎችን ያካተቱ በመሆናቸው ለሀገራችን የኢኮኖሚ እድገት አዎንታዊ አስተዋጽኦ ያበረክታሉ።
ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የችግኝ ተከላ ዘመቻዎች ሕዝቡ ባደረገው ከፍተኛ ተሳትፎ መርሐ ግብሩ ከአካባቢ ጥበቃ ባለፈ የሀገራዊ አንድነት መገለጫ መሆን ችሏል።
800 ሚሊየን ችግኞችን በአንድ ጀንበር የመትከል ዘመቻው ለኢትዮጵያ የአረንጓዴ ልማት፣ የአየር ንብረት ተጽዕኖን ለመቋቋም፣ ለምግብ ዋስትናና ለትውልድ ተሻጋሪ የተፈጥሮ ሀብት ግንባታ የሚያበረክተውን ድርሻ የበለጠ የሚያጎላ ነው።
እያንዳንዱ ዜጋ ከጫፍ እስከ ጫፍ በመነሳት የድርሻውን እንዲወጣ የሚጠይቀው ይህ ሀገራዊ ጥሪ በከተማም ሆነ በገጠር የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን በማለዳው በመውጣት የራሳቸውን ታሪካዊ ዐሻራ እንዲያኖሩ በር የከፈተ ሆኗል።
ይህ እቅድ የቁጥር ጉዳይ ብቻ ሳይሆን የጽናት፣ የህብረትና የልማት ታላቅ መገለጫ በመሆኑ ኢትዮጵያውያን በተፈጥሮ ሀብታቸው ላይ አዲስ ሕይወት የሚዘሩበት፣ ለቀጣዩ ትውልድ ለም እና አረንጓዴ ሀገር የሚያስረክቡበት ታሪካዊ አጋጣሚ ነው።
ችግኞችን ከመትከል ባለፈ የመንከባከብና የመጠበቅ ባሕልን ማሳደግ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር ዋነኛ ምሰሶ በመሆኑ እያንዳንዱ የተተከለ ችግኝ ጸድቆ ለፍሬ እንዲበቃ ሁሉም አካላት የተቀናጀ ጥረትና ክትትል ማድረግ ይጠበቅባቸዋል።
3 days ago
የሐረማያ ሐይቅ ማንሰራራት፦ የአረንጓዴ ዐሻራ ትሩፋት ማሳያ
********************
በተፈጥሯዊ እና በሰው ሰራሽ ምክንያት ሙሉ በሙሉ ደርቆ ወደ አቧራማ ሜዳነት ተቀይሮ የነበረው ታሪካዊው ሐረማያ ሐይቅ አሁን ላይ በዘላቂ የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ እና በአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር አማካኝነት ወደ ቀድሞ ይዘቱ ተመልሷል።
የሐረማያ ሐይቅ በዚህ መልኩ ማገገሙ በዕቅድ እና በጋራ ጥረት የተራቆቱ ሌሎች ተፋሰሶችንም ወደነበሩበት ሁኔታ መመለስ እንደሚቻል የሚያሳይ ሕያው ማረጋገጫ ሆኗል።
ሐረማያ ሐይቅ ለሐረማያ እና ለሐረር ከተሞች፣ ለሐረማያ ዩኒቨርሲቲ እንዲሁም ለአካባቢው ነዋሪዎች ዋነኛ የንጹህ መጠጥ ውኃና የግብርና መሠረት የነበረ ቢሆንም፣ በከፍተኛ የደን መጨፍጨፍ እና በደለል መሞላት ምክንያት ውኃ የመያዝ አቅሙን አጥቶ ተስፋ ተቆርጦበት የነበረ ነው።
ሆኖም ባለፉት ዓመታት በሐይቁ የላይኛው ተፋሰስ አካባቢዎች በተከናወነ የችግኝ ተከላ እና የእርከን ሥራ ወደ ሐይቁ ይገባ የነበረውን ከፍተኛ ደለል ከምንጩ መግታት ተችሏል።
በሌላ በኩል በሐይቁ ዙሪያ በተሠሩ የውኃ ማሳረፊያዎች አማካኝነት የዝናብ ውኃ ወደ መሬት እንዲሰርግ በማድረግ የሐይቁን ከርሰ ምድር ውኃ ክምችት እንዲጨምር ሆኗል።
በዚህም ሐይቁ ዳግም ውኃ መያዝ በመጀመሩ ቀደም ሲል አካባቢውን ለቀው የተሰደዱ በርካታ አእዋፍ፣ የጠፉ ዓሳዎች እና ሌሎች የውኃ ሕይወቶች እየተመለሱ ይገኛሉ።
የሐረማያ ሐይቅ ተሞክሮ ነገ የሚካሄደው የአንድ ጀምበር አረንጓዴ ዐሻራ ሀገር አቀፍ ንቅናቄ ተራ የችግኝ ተከላ መርሐ ግብር ሳይሆን የታመመ ተፈጥሮን አክሞ የማዳን ሀገራዊ ጥረት መሆኑን የሚያስረግጥ ነው።
ይህ ተሞክሮ እያንዳንዱ ችግኝ የተራቆቱ አካባቢዎችን መልሶ የማቋቋም፣ የውኃ አካላትን የመታደግ እና የተጎዳ ተፈጥሮን የማከም ወሳኝ ድርሻ ይጫወታል።
ነገ በአንድ ጀምበር በጋራ የምናኖረው አረንጓዴ ዐሻራ የዛሬን የተፈጥሮ ቁስል እያከመ፣ የነገዋን ኢትዮጵያ በውኃ ሀብት እና በልምላሜ ሙሉ የሚያደርግ ታሪካዊ ተግባር ነው።
በሐና ምንዳሁን
#ethiopia #climateaction #greenlegacy #800milliontrees #lakeharamaya #ebc #ebcdotstream
********************
በተፈጥሯዊ እና በሰው ሰራሽ ምክንያት ሙሉ በሙሉ ደርቆ ወደ አቧራማ ሜዳነት ተቀይሮ የነበረው ታሪካዊው ሐረማያ ሐይቅ አሁን ላይ በዘላቂ የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ እና በአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር አማካኝነት ወደ ቀድሞ ይዘቱ ተመልሷል።
የሐረማያ ሐይቅ በዚህ መልኩ ማገገሙ በዕቅድ እና በጋራ ጥረት የተራቆቱ ሌሎች ተፋሰሶችንም ወደነበሩበት ሁኔታ መመለስ እንደሚቻል የሚያሳይ ሕያው ማረጋገጫ ሆኗል።
ሐረማያ ሐይቅ ለሐረማያ እና ለሐረር ከተሞች፣ ለሐረማያ ዩኒቨርሲቲ እንዲሁም ለአካባቢው ነዋሪዎች ዋነኛ የንጹህ መጠጥ ውኃና የግብርና መሠረት የነበረ ቢሆንም፣ በከፍተኛ የደን መጨፍጨፍ እና በደለል መሞላት ምክንያት ውኃ የመያዝ አቅሙን አጥቶ ተስፋ ተቆርጦበት የነበረ ነው።
ሆኖም ባለፉት ዓመታት በሐይቁ የላይኛው ተፋሰስ አካባቢዎች በተከናወነ የችግኝ ተከላ እና የእርከን ሥራ ወደ ሐይቁ ይገባ የነበረውን ከፍተኛ ደለል ከምንጩ መግታት ተችሏል።
በሌላ በኩል በሐይቁ ዙሪያ በተሠሩ የውኃ ማሳረፊያዎች አማካኝነት የዝናብ ውኃ ወደ መሬት እንዲሰርግ በማድረግ የሐይቁን ከርሰ ምድር ውኃ ክምችት እንዲጨምር ሆኗል።
በዚህም ሐይቁ ዳግም ውኃ መያዝ በመጀመሩ ቀደም ሲል አካባቢውን ለቀው የተሰደዱ በርካታ አእዋፍ፣ የጠፉ ዓሳዎች እና ሌሎች የውኃ ሕይወቶች እየተመለሱ ይገኛሉ።
የሐረማያ ሐይቅ ተሞክሮ ነገ የሚካሄደው የአንድ ጀምበር አረንጓዴ ዐሻራ ሀገር አቀፍ ንቅናቄ ተራ የችግኝ ተከላ መርሐ ግብር ሳይሆን የታመመ ተፈጥሮን አክሞ የማዳን ሀገራዊ ጥረት መሆኑን የሚያስረግጥ ነው።
ይህ ተሞክሮ እያንዳንዱ ችግኝ የተራቆቱ አካባቢዎችን መልሶ የማቋቋም፣ የውኃ አካላትን የመታደግ እና የተጎዳ ተፈጥሮን የማከም ወሳኝ ድርሻ ይጫወታል።
ነገ በአንድ ጀምበር በጋራ የምናኖረው አረንጓዴ ዐሻራ የዛሬን የተፈጥሮ ቁስል እያከመ፣ የነገዋን ኢትዮጵያ በውኃ ሀብት እና በልምላሜ ሙሉ የሚያደርግ ታሪካዊ ተግባር ነው።
በሐና ምንዳሁን
#ethiopia #climateaction #greenlegacy #800milliontrees #lakeharamaya #ebc #ebcdotstream
3 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) ‹‹የሱዳንና የኤርትራ አጋርነት ለአፍሪካ ቀንድና ቀይ ባህር መረጋጋት ከፍተኛ ሚና ይጫወታል፡፡›› ሲሉ በኤርትራ የሱዳን አምባሳደር ገለፁ፡፡ በኤርትራ የሱዳን አምባሳደር የሆኑት ኦሳማ አህመድ አደል ባሪ ዛሬ ባሰራጩት ዘለግ ያለ ፅሁፍ የሁለቱን አገራት ግንኙነት ጠቀሜታ አጉልተው ለማሳየት ጥረዋል፡፡ በሱዳን ሆራይዘን ጋዜጣ ላይ በሰፈረው በዚህ ፅሁፋቸው ‹‹ቀይ ባህርና የአፍሪካ ቀንድ በአሁኑ ጊዜ በፍጥነት በሚለዋወጥ ጂኦፖለቲካዊ ባህርይና በመርከቦች ጉዞ፣ በአቅርቦት ሰንሰለት፣ በነዳጅ ሀብትና በተፈጥሮ ሀብት ላይ በሚደረግ ፉክክር ወሳኝ ምእራፍ ውስጥ ይገኛሉ›› በማለት ጀምረዋል፡፡
አስከትለውም ከዚህ በመነሳት ከክልላዊ አጋርነት በተሻለ ሰፋ ያሉ የደህንነት፣ የልማትና ዘላቂ መረጋጋትን አላማው ያደረገ ስትራቴጂያዊ ጥምረት እንደሚያስፈልግ አስረድተዋል፡፡ አምባሳደሩ ሲቀጥሉም ‹‹ከዚህ አንፃር የሱዳንና ኤርትራ ስትራቴጂያዊ አጋርነት የተረጋጋ ቀጣናዊ የሀይል ሚዛን እንዲኖር የሚያስችል ትልቅ መሰረት ነው›› ያሉ ሲሆን ሁለቱ አገራት በቀይ ባህርና በአፍሪካ ቀንድ ዙሪያ የጋራ ፍላጎት እንዳላቸው ገልፀዋል፡፡ ጨምረውም ‹‹ሱዳን በቀይ ባህር ዳርቻዋ በኩል ሰሜን አፍሪካን ከምስራቅና ከመካከለኛው አፍሪካ ጋር የምታገናኝ ድልድይ ናት፡፡
እንዲሁም ባላት የግብርና፣ የውሀና የማእድን ሀብቶች በቀጠናው ውስጥ ትልቅ የልማት ሞተር ሆና ማገልገል ትችላለች፡፡ በሌላ በኩል ኤርትራ ደግሞ በቀይ ባህር ላይ ልዩ የሆነ ጂኦግራፊያዊ አቀማመጥ ያላት ከመሆኑም በላይ ሰፊ የባህር ዳርቻና ተስፋ ሰጪ ወደቦችን የያዘች ናት፡፡ ስለዚህም እነዚህ ጉዳዮች ኢኮኖሚያዊ ውህደት ለመፍጠርና በቀጠናው ውስጥ የተረጋጋ ፖለቲካ ለመፍጠር ምሰሶ ሆነው ሊያገለግሉ ይችላሉ›› በማለት ገልፀው ሁለቱ አገራት ዘላቂነት ያለውና ረጅም ራእይ የሰነቀ ስትራቴጂያዊ አጋርነት መፍጠራቸውን አስረድተዋል፡፡
አስከትለውም ከዚህ በመነሳት ከክልላዊ አጋርነት በተሻለ ሰፋ ያሉ የደህንነት፣ የልማትና ዘላቂ መረጋጋትን አላማው ያደረገ ስትራቴጂያዊ ጥምረት እንደሚያስፈልግ አስረድተዋል፡፡ አምባሳደሩ ሲቀጥሉም ‹‹ከዚህ አንፃር የሱዳንና ኤርትራ ስትራቴጂያዊ አጋርነት የተረጋጋ ቀጣናዊ የሀይል ሚዛን እንዲኖር የሚያስችል ትልቅ መሰረት ነው›› ያሉ ሲሆን ሁለቱ አገራት በቀይ ባህርና በአፍሪካ ቀንድ ዙሪያ የጋራ ፍላጎት እንዳላቸው ገልፀዋል፡፡ ጨምረውም ‹‹ሱዳን በቀይ ባህር ዳርቻዋ በኩል ሰሜን አፍሪካን ከምስራቅና ከመካከለኛው አፍሪካ ጋር የምታገናኝ ድልድይ ናት፡፡
እንዲሁም ባላት የግብርና፣ የውሀና የማእድን ሀብቶች በቀጠናው ውስጥ ትልቅ የልማት ሞተር ሆና ማገልገል ትችላለች፡፡ በሌላ በኩል ኤርትራ ደግሞ በቀይ ባህር ላይ ልዩ የሆነ ጂኦግራፊያዊ አቀማመጥ ያላት ከመሆኑም በላይ ሰፊ የባህር ዳርቻና ተስፋ ሰጪ ወደቦችን የያዘች ናት፡፡ ስለዚህም እነዚህ ጉዳዮች ኢኮኖሚያዊ ውህደት ለመፍጠርና በቀጠናው ውስጥ የተረጋጋ ፖለቲካ ለመፍጠር ምሰሶ ሆነው ሊያገለግሉ ይችላሉ›› በማለት ገልፀው ሁለቱ አገራት ዘላቂነት ያለውና ረጅም ራእይ የሰነቀ ስትራቴጂያዊ አጋርነት መፍጠራቸውን አስረድተዋል፡፡
3 days ago
የአረንጓዴ ዐሻራ የሰባት ዓመታት ሰባት አንኳር ስኬቶች
*************
አረንጓዴ ዐሻራ በኢትዮጵያ ምድር ከተጀመረበት ጊዜ አንስቶ ባለፉት ሰባት ዓመታት፣ ሀገራችንን ከአፈር መሸርሸር እና ከበረሃማነት የመታደግ ሀገራዊ ራዕይ ብቻ ሳይሆን፤ የምድርን ሕይወት የሚያድስ፣ የዜጎችን ሥነ-ልቦናዊ አስተሳሰብ የሚቀርጽ እና ኢኮኖሚያዊ አቅም የሚገነባ ታላቅ ሕዝባዊ ንቅናቄ ሆኖ ዘልቋል።
ይህ ሀገራዊ የሕልውና ጥረት ከሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ ስትራቴጂዎች ጋር ተናብቦ ባለፉት ሰባት ዓመታት ያስመዘገባቸው ሰባት ዋና ዋና ተጨባጭ ስኬቶች እንደሚከተለው ተተንትነዋል።
1. የችግኝ ብዛትን ከጽድቀት ምጣኔ ጋር ያጣመረ አዲስ ታሪካዊ ሽግግር
ባለፉት ሰባት ዓመታት በቢሊዮኖች የሚቆጠሩ ችግኞች መተከላቸው ብቻ ሳይሆን፣ የተከላው ዋና ትኩረት ወደ ጥራት እና ድኅረ-ተከላ እንክብካቤ በማደጉ የችግኞች ጽድቀት ምጣኔ ከ80 በመቶ በላይ ማደግ ችሏል።
ይህም ቀደም ሲል የነበረውን "መተከል እንጂ አለመጽደቅ" የሚል የብክነት ታሪክን በመቀየር በቆላ እና በደጋ አካባቢዎች የተጎዱ መሬቶች በፍጥነት አረንጓዴ እንዲለብሱ እና ሥነ-ምኅዳራዊ ሚዛን እንዲጠበቅ አድርጓል።
2. ከአካባቢ ጥበቃ ወደ የምግብ ዋስትና የተደረገ መዋቅራዊ የኢኮኖሚ ሽግግር
አረንጓዴ ዐሻራ ከተፈጥሮ የደን ዛፎች ባሻገር እንደ አቮካዶ፣ ማንጎ፣ ፓፓያ፣ አፕል እና ቡና ያሉ ፍሬያማ ተክሎችን በስፋት አካትቷል።
ይህ ስትራቴጂያዊ እርምጃ ፕሮጀክቱን ከአካባቢ ጥበቃ ባለፈ የቤተሰብ የምግብ ዋስትናን የሚያረጋግጥ እና አባወራዎችን የገበያ ተጠቃሚ የሚያደርግ፣ ብሎም የሀገራችን የግብርና ምርት የወጪ ንግድ የሚያሳድግ የኢኮኖሚ ሞተር አድርጎታል።
ይህም የአካባቢ ጥበቃን ከዜጎች የዕለት ተዕለት ኑሮ ማሻሻል ግብ ጋር በማስተሳሰር ዘላቂነቱ የተረጋገጠ የልማት ምሰሶ እንዲሆን አስችሎታል።
3. የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ግንባታ እና የወጣቶች የሥራ ዕድል ፈጠራ
በመላ ሀገራችን የተቋቋሙት በዐሥር ሺዎች የሚቆጠሩ የችግኝ ማፍያ ጣቢያዎች ለብዙ ዜጎች፣ በተለይም ለወጣቶች እና ለሴቶች አዲስ እና ዘላቂ የገቢ ምንጭ ሆነዋል።
ችግኝ ማፍላት፣ መንከባከብ እና ለገበያ ማቅረብ በራሱ አዲስ የኢንቨስትመንት ዘርፍ እና የሥራ ዕድል በመፍጠር፣ የሀገራችንን የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ጅማሮ በጠንካራ መሠረት ላይ አኑሮታል።
ችግኞች ከተተከሉ በኋላ የሚደረገው ጥበቃ እና ክብካቤም በርካታ ወጣቶችን ተጠቃሚ ያደረገ ቋሚ የሥራ ዘርፍ መሆን ችሏል።
4. የውኃ ሀብት እና የታላላቅ ሀገራዊ የልማት ፕሮጀክቶች ዋስትና
በስፋት የተከናወነው የደን ልማት እና የአፈር ጥበቃ ሥራ የአፈር መሸርሸርን በመቀነስ፣ እንደ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ያሉ ሀገራዊ የሃይድሮ ኤሌክትሪክ ማመንጫዎች በደለል እንዳይሞሉ የመከላከል ታሪካዊ ሚና ተጫውቷል።
በተጨማሪም የከርሰ ምድር ውኃ መጠን እንዲያገግም እና የደረቁ የምንጭ ውኃዎች መልሰው እንዲፈልቁ በማድረግ አስተማማኝ የውኃ ዋስትናን እያረጋገጠ ይገኛል።
ይህ ታላላቅ መሠረተ ልማቶችን የመጠበቅ አቅም ለኢትዮጵያ ብልጽግና ብቻ ሳይሆን፣ ሀገራችን የውኃ ምንጭ ለሆነችላቸው የታችኛው ተፋሰስ ሀገራት ጭምር ትልቅ ትሩፋት ነው።
5. አረንጓዴ ዲፕሎማሲ እና የቀጣናዊ ትሥሥር ማጠናከሪያ
ኢትዮጵያ ያዘጋጀቻቸውን ችግኞች እንደ ጂቡቲ፣ ሶማሊያ፣ ደቡብ ሱዳን እና ኬንያ ላሉት ጎረቤት ሀገራት በማጋራት፣ የምሥራቅ አፍሪካን እና የአፍሪካ ቀንድን የቀጣና አየር ንብረት ለውጥ ተግዳሮት በጋራ የመከላከል መሪነት ሚናዋን በተግባር አሳይታለች።
ይህም አረንጓዴ ዐሻራን የድንበር ተሻጋሪ ዲፕሎማሲ፣ የቀጠናው ሰላም እና የጋራ ልማት መሣሪያ አድርጎታል።
በርካታ የአፍሪካ ሀገራትም የኢትዮጵያን ፈለግ በመከተል የአረንጓዴ ልማትን በሀገሮቻቸው እያስፋፉ ይገኛሉ።
ከዚህ ባሻገር፣ ኢትዮጵያ ባመጣቻቸው ተጨባጭ ስኬቶች “ዘላቂ የደን ልማት አያያዝ እና አጠቃቀም” በሚል ዘርፍ ከዓለም የምግብ እና እርሻ ድርጅት (FAO) ከፍተኛ እውቅናን አግኝታለች።
6. የከተሞች ሥነ-ምኅዳር መታደስ እና የኮሪደር ልማት ውበት
አረንጓዴ ዐሻራ በገጠር ተራራዎች ብቻ ተወስኖ ሳይቀር ወደ ከተሞች በመግባት የዘመናዊ ፓርኮች ግንባታ፣ የከተማ አረንጓዴ ልማት እና አሁን ላይ በስፋት እየተተገበረ ላለው የኮሪደር ልማት ዋነኛ አካል ሆኗል።
ይህም የከተሞችን የአየር ጥራት በከፍተኛ ደረጃ ከመጨመሩም በላይ፣ የሥነ-ሕይወት ስብጥርን ወደ ነበረበት በመመለስ እና ለዜጎች ምቹ የመዝናኛ እና የኑሮ አካባቢን በመፍጠር የከተሞቻችንን ገጽታ ሙሉ በሙሉ በመለወጥ ላይ ይገኛል።
7. ሕዝባዊ ንቅናቄ እና የዜግነት አገልግሎት ባህል ግንባታ
በአንድ ጀምበር በመቶ ሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎች በነቂስ ወጥተው ችግኝ የመተከል ልምዳቸው፣ የአካባቢ ጥበቃን ከዘመቻነት አውጥቶ የባህል እና የዜግነት ግዴታ አካል አድርጎታል።
ይህም የሕዝባዊ ወንድማማችነትን ያጠናከረ እና የአካባቢ ጥበቃ ግንዛቤን በማሳደግ ለቀጣዩ ትውልድ የሚሻገር እጅግ ግዙፍ ማኅበራዊ እና ሥነ-ልቦናዊ ስኬት ነው።
በአጠቃላይ አረንጓዴ ዐሻራ ባለፉት ሰባት ዓመታት የተፈጥሮ ሀብታችንን ከመመለስ አልፎ ሀገራዊ አንድነትን ያጠናከረ፣ የማክሮ ኢኮኖሚ አቅማችንን የገነባ እና ኢትዮጵያን በዓለም አቀፍ መድረክ ለአየር ንብረት ለውጥ መፍትሔ አቅራቢ ሀገር ያደረገ አንጸባራቂ አዲስ የታሪክ ምዕራፍ ነው።
በለሚ ታደሰ
#ethiopia #ebc #greenlegacy #climateaction #greendiplomacy #greeneconomy
*************
አረንጓዴ ዐሻራ በኢትዮጵያ ምድር ከተጀመረበት ጊዜ አንስቶ ባለፉት ሰባት ዓመታት፣ ሀገራችንን ከአፈር መሸርሸር እና ከበረሃማነት የመታደግ ሀገራዊ ራዕይ ብቻ ሳይሆን፤ የምድርን ሕይወት የሚያድስ፣ የዜጎችን ሥነ-ልቦናዊ አስተሳሰብ የሚቀርጽ እና ኢኮኖሚያዊ አቅም የሚገነባ ታላቅ ሕዝባዊ ንቅናቄ ሆኖ ዘልቋል።
ይህ ሀገራዊ የሕልውና ጥረት ከሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ ስትራቴጂዎች ጋር ተናብቦ ባለፉት ሰባት ዓመታት ያስመዘገባቸው ሰባት ዋና ዋና ተጨባጭ ስኬቶች እንደሚከተለው ተተንትነዋል።
1. የችግኝ ብዛትን ከጽድቀት ምጣኔ ጋር ያጣመረ አዲስ ታሪካዊ ሽግግር
ባለፉት ሰባት ዓመታት በቢሊዮኖች የሚቆጠሩ ችግኞች መተከላቸው ብቻ ሳይሆን፣ የተከላው ዋና ትኩረት ወደ ጥራት እና ድኅረ-ተከላ እንክብካቤ በማደጉ የችግኞች ጽድቀት ምጣኔ ከ80 በመቶ በላይ ማደግ ችሏል።
ይህም ቀደም ሲል የነበረውን "መተከል እንጂ አለመጽደቅ" የሚል የብክነት ታሪክን በመቀየር በቆላ እና በደጋ አካባቢዎች የተጎዱ መሬቶች በፍጥነት አረንጓዴ እንዲለብሱ እና ሥነ-ምኅዳራዊ ሚዛን እንዲጠበቅ አድርጓል።
2. ከአካባቢ ጥበቃ ወደ የምግብ ዋስትና የተደረገ መዋቅራዊ የኢኮኖሚ ሽግግር
አረንጓዴ ዐሻራ ከተፈጥሮ የደን ዛፎች ባሻገር እንደ አቮካዶ፣ ማንጎ፣ ፓፓያ፣ አፕል እና ቡና ያሉ ፍሬያማ ተክሎችን በስፋት አካትቷል።
ይህ ስትራቴጂያዊ እርምጃ ፕሮጀክቱን ከአካባቢ ጥበቃ ባለፈ የቤተሰብ የምግብ ዋስትናን የሚያረጋግጥ እና አባወራዎችን የገበያ ተጠቃሚ የሚያደርግ፣ ብሎም የሀገራችን የግብርና ምርት የወጪ ንግድ የሚያሳድግ የኢኮኖሚ ሞተር አድርጎታል።
ይህም የአካባቢ ጥበቃን ከዜጎች የዕለት ተዕለት ኑሮ ማሻሻል ግብ ጋር በማስተሳሰር ዘላቂነቱ የተረጋገጠ የልማት ምሰሶ እንዲሆን አስችሎታል።
3. የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ግንባታ እና የወጣቶች የሥራ ዕድል ፈጠራ
በመላ ሀገራችን የተቋቋሙት በዐሥር ሺዎች የሚቆጠሩ የችግኝ ማፍያ ጣቢያዎች ለብዙ ዜጎች፣ በተለይም ለወጣቶች እና ለሴቶች አዲስ እና ዘላቂ የገቢ ምንጭ ሆነዋል።
ችግኝ ማፍላት፣ መንከባከብ እና ለገበያ ማቅረብ በራሱ አዲስ የኢንቨስትመንት ዘርፍ እና የሥራ ዕድል በመፍጠር፣ የሀገራችንን የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ጅማሮ በጠንካራ መሠረት ላይ አኑሮታል።
ችግኞች ከተተከሉ በኋላ የሚደረገው ጥበቃ እና ክብካቤም በርካታ ወጣቶችን ተጠቃሚ ያደረገ ቋሚ የሥራ ዘርፍ መሆን ችሏል።
4. የውኃ ሀብት እና የታላላቅ ሀገራዊ የልማት ፕሮጀክቶች ዋስትና
በስፋት የተከናወነው የደን ልማት እና የአፈር ጥበቃ ሥራ የአፈር መሸርሸርን በመቀነስ፣ እንደ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ያሉ ሀገራዊ የሃይድሮ ኤሌክትሪክ ማመንጫዎች በደለል እንዳይሞሉ የመከላከል ታሪካዊ ሚና ተጫውቷል።
በተጨማሪም የከርሰ ምድር ውኃ መጠን እንዲያገግም እና የደረቁ የምንጭ ውኃዎች መልሰው እንዲፈልቁ በማድረግ አስተማማኝ የውኃ ዋስትናን እያረጋገጠ ይገኛል።
ይህ ታላላቅ መሠረተ ልማቶችን የመጠበቅ አቅም ለኢትዮጵያ ብልጽግና ብቻ ሳይሆን፣ ሀገራችን የውኃ ምንጭ ለሆነችላቸው የታችኛው ተፋሰስ ሀገራት ጭምር ትልቅ ትሩፋት ነው።
5. አረንጓዴ ዲፕሎማሲ እና የቀጣናዊ ትሥሥር ማጠናከሪያ
ኢትዮጵያ ያዘጋጀቻቸውን ችግኞች እንደ ጂቡቲ፣ ሶማሊያ፣ ደቡብ ሱዳን እና ኬንያ ላሉት ጎረቤት ሀገራት በማጋራት፣ የምሥራቅ አፍሪካን እና የአፍሪካ ቀንድን የቀጣና አየር ንብረት ለውጥ ተግዳሮት በጋራ የመከላከል መሪነት ሚናዋን በተግባር አሳይታለች።
ይህም አረንጓዴ ዐሻራን የድንበር ተሻጋሪ ዲፕሎማሲ፣ የቀጠናው ሰላም እና የጋራ ልማት መሣሪያ አድርጎታል።
በርካታ የአፍሪካ ሀገራትም የኢትዮጵያን ፈለግ በመከተል የአረንጓዴ ልማትን በሀገሮቻቸው እያስፋፉ ይገኛሉ።
ከዚህ ባሻገር፣ ኢትዮጵያ ባመጣቻቸው ተጨባጭ ስኬቶች “ዘላቂ የደን ልማት አያያዝ እና አጠቃቀም” በሚል ዘርፍ ከዓለም የምግብ እና እርሻ ድርጅት (FAO) ከፍተኛ እውቅናን አግኝታለች።
6. የከተሞች ሥነ-ምኅዳር መታደስ እና የኮሪደር ልማት ውበት
አረንጓዴ ዐሻራ በገጠር ተራራዎች ብቻ ተወስኖ ሳይቀር ወደ ከተሞች በመግባት የዘመናዊ ፓርኮች ግንባታ፣ የከተማ አረንጓዴ ልማት እና አሁን ላይ በስፋት እየተተገበረ ላለው የኮሪደር ልማት ዋነኛ አካል ሆኗል።
ይህም የከተሞችን የአየር ጥራት በከፍተኛ ደረጃ ከመጨመሩም በላይ፣ የሥነ-ሕይወት ስብጥርን ወደ ነበረበት በመመለስ እና ለዜጎች ምቹ የመዝናኛ እና የኑሮ አካባቢን በመፍጠር የከተሞቻችንን ገጽታ ሙሉ በሙሉ በመለወጥ ላይ ይገኛል።
7. ሕዝባዊ ንቅናቄ እና የዜግነት አገልግሎት ባህል ግንባታ
በአንድ ጀምበር በመቶ ሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎች በነቂስ ወጥተው ችግኝ የመተከል ልምዳቸው፣ የአካባቢ ጥበቃን ከዘመቻነት አውጥቶ የባህል እና የዜግነት ግዴታ አካል አድርጎታል።
ይህም የሕዝባዊ ወንድማማችነትን ያጠናከረ እና የአካባቢ ጥበቃ ግንዛቤን በማሳደግ ለቀጣዩ ትውልድ የሚሻገር እጅግ ግዙፍ ማኅበራዊ እና ሥነ-ልቦናዊ ስኬት ነው።
በአጠቃላይ አረንጓዴ ዐሻራ ባለፉት ሰባት ዓመታት የተፈጥሮ ሀብታችንን ከመመለስ አልፎ ሀገራዊ አንድነትን ያጠናከረ፣ የማክሮ ኢኮኖሚ አቅማችንን የገነባ እና ኢትዮጵያን በዓለም አቀፍ መድረክ ለአየር ንብረት ለውጥ መፍትሔ አቅራቢ ሀገር ያደረገ አንጸባራቂ አዲስ የታሪክ ምዕራፍ ነው።
በለሚ ታደሰ
#ethiopia #ebc #greenlegacy #climateaction #greendiplomacy #greeneconomy
3 days ago
በሚቀጥሉት 5 ዓመታት ለትምህርት ጥራት እና ውጤታማነት መጠናከር ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል - የትምህርት ሚኒስቴር
**************************
7ኛው የትምህርት ዘርፍ ልማት ፕሮግራም (ESDP VII) ረቂቅ ዕቅድ ላይ ውይይት ማድረጉን የትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ።
በአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ የምክክር መድረክ ላይ በስትራቴጂያዊ ጉዳዮች የቀረበው 7ኛው የትምህርት ዘርፍ ልማት ፕሮግራም (ESDP VII 2026/27 to 2030/31) ረቂቅ ዕቅድ፣ በሚቀጥሉት አምስት ዓመታት የትምህርት ጥራትና ውጤታማነትን ማጠናከር ዋና ትኩረት እንደሚሆን አመላክቷል።
በረቂቅ ዕቅዱ መሠረት፣ የትምህርት ጥራትን እና ተገቢነትን ለማረጋገጥ ቀደም ሲል የተጀመሩ ሥራዎችን በአዳዲስ አሠራሮች ማጠናከር፣ የትምህርትን ውጤት በተጨባጭ መለካት እና በትምህርት ዘርፍ የቴክኖሎጂ አጠቃቀምን ማሳደግ ቅድሚያ የተሰጣቸው ጉዳዮች መሆናቸው ተገልጿል።
ፕሮግራሙ አዲሱን ሥርዓተ ትምህርት በውጤታማነት መተግበር፣ ምዘናን በብቃት ላይ የተመሠረተ እንዲሆን ማድረግ፣ የተማሪዎችን የመማር ውጤት ማሻሻል እንዲሁም በቋንቋ፣ በሒሳብ እና በሳይንስ ትምህርቶች ያላቸውን ብቃት ማሳደግን እንደ ዋና ተግባራት አካቷል።
በተጨማሪም የዲጂታል ትምህርትን ማስፋፋት፣ የብሔራዊ ፈተናዎችን ማዘመን፣ በቴክኒክ እና ሙያ ሥልጠና (TVET) እና በከፍተኛ ትምህርት መካከል ያለውን ቅንጅት ማጠናከር፣ የመምህራንን ሙያዊ ብቃት እና ማበረታቻ ማሻሻል፣ እንዲሁም የመምህራን ማሠልጠኛ ኮሌጆችን እና ዩኒቨርሲቲዎችን ማጠናከር በዕቅዱ ውስጥ ተካትተዋል።
ረቂቅ ዕቅዱ የትምህርት ጥራት፣ ተገቢነትን ተደራሽነትን እና ፍትሐዊነትን ማረጋገጥ፣ በተፈጥሮ እና በሰው ሠራሽ አደጋዎች ምክንያት የተጎዱ የትምህርት ማኅበረሰቦችን መልሶ ማቋቋም፣ ትምህርትን ሳይቋረጥ እንዲዘልቅ የሚያስችል ሥርዓት መገንባት፣ እንዲሁም ልዩ ፍላጎት ያላቸውን ተማሪዎች እና የሴት ተማሪዎችን የትምህርት ተሳትፎ እና ውጤታማነት ማረጋገጥ ላይም ልዩ ትኩረት መስጠቱን ያመለክታል።
7ኛው የትምህርት ዘርፍ ልማት ፕሮግራም (ESDP VII) ረቂቅ ዕቅድ በምክክር መድረኩ ላይ ቀርቦ፣ በክልል እና በከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊዎች፣ እንዲሁም በዘርፉ ባለድርሻ አካላት ሰፊ ውይይት የተደረገበት መሆኑን ከትምህርት ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።
#ethiopia #ebc #education #ministryofeducation #educationquality
**************************
7ኛው የትምህርት ዘርፍ ልማት ፕሮግራም (ESDP VII) ረቂቅ ዕቅድ ላይ ውይይት ማድረጉን የትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ።
በአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ የምክክር መድረክ ላይ በስትራቴጂያዊ ጉዳዮች የቀረበው 7ኛው የትምህርት ዘርፍ ልማት ፕሮግራም (ESDP VII 2026/27 to 2030/31) ረቂቅ ዕቅድ፣ በሚቀጥሉት አምስት ዓመታት የትምህርት ጥራትና ውጤታማነትን ማጠናከር ዋና ትኩረት እንደሚሆን አመላክቷል።
በረቂቅ ዕቅዱ መሠረት፣ የትምህርት ጥራትን እና ተገቢነትን ለማረጋገጥ ቀደም ሲል የተጀመሩ ሥራዎችን በአዳዲስ አሠራሮች ማጠናከር፣ የትምህርትን ውጤት በተጨባጭ መለካት እና በትምህርት ዘርፍ የቴክኖሎጂ አጠቃቀምን ማሳደግ ቅድሚያ የተሰጣቸው ጉዳዮች መሆናቸው ተገልጿል።
ፕሮግራሙ አዲሱን ሥርዓተ ትምህርት በውጤታማነት መተግበር፣ ምዘናን በብቃት ላይ የተመሠረተ እንዲሆን ማድረግ፣ የተማሪዎችን የመማር ውጤት ማሻሻል እንዲሁም በቋንቋ፣ በሒሳብ እና በሳይንስ ትምህርቶች ያላቸውን ብቃት ማሳደግን እንደ ዋና ተግባራት አካቷል።
በተጨማሪም የዲጂታል ትምህርትን ማስፋፋት፣ የብሔራዊ ፈተናዎችን ማዘመን፣ በቴክኒክ እና ሙያ ሥልጠና (TVET) እና በከፍተኛ ትምህርት መካከል ያለውን ቅንጅት ማጠናከር፣ የመምህራንን ሙያዊ ብቃት እና ማበረታቻ ማሻሻል፣ እንዲሁም የመምህራን ማሠልጠኛ ኮሌጆችን እና ዩኒቨርሲቲዎችን ማጠናከር በዕቅዱ ውስጥ ተካትተዋል።
ረቂቅ ዕቅዱ የትምህርት ጥራት፣ ተገቢነትን ተደራሽነትን እና ፍትሐዊነትን ማረጋገጥ፣ በተፈጥሮ እና በሰው ሠራሽ አደጋዎች ምክንያት የተጎዱ የትምህርት ማኅበረሰቦችን መልሶ ማቋቋም፣ ትምህርትን ሳይቋረጥ እንዲዘልቅ የሚያስችል ሥርዓት መገንባት፣ እንዲሁም ልዩ ፍላጎት ያላቸውን ተማሪዎች እና የሴት ተማሪዎችን የትምህርት ተሳትፎ እና ውጤታማነት ማረጋገጥ ላይም ልዩ ትኩረት መስጠቱን ያመለክታል።
7ኛው የትምህርት ዘርፍ ልማት ፕሮግራም (ESDP VII) ረቂቅ ዕቅድ በምክክር መድረኩ ላይ ቀርቦ፣ በክልል እና በከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊዎች፣ እንዲሁም በዘርፉ ባለድርሻ አካላት ሰፊ ውይይት የተደረገበት መሆኑን ከትምህርት ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።
#ethiopia #ebc #education #ministryofeducation #educationquality
Sponsored by
Surafel
3 days ago
የቀድሞው የዓለም ባንክ ፕሬዝዳንት የኢትዮጵያ የምንዛሬ ሪፎርም ድህነትን አባብሷል አሉ።
የቀድሞው የዓለም ባንክ ፕሬዝዳንት ዳቪድ ማልፓስ የኢትዮጵያ ብር መዳከም እና የውጭ ምንዛሬ ማሻሻያዎች ድህነትን በከፍተኛ ሁኔታ ማባባሳቸውን በመግለጽ፤ በብር ደመወዝ የሚከፈላቸው ሰዎች «ገቢያቸው እጅግ ቀንሷል» ሲሉ ተናግረዋል።
በተቃራኒው ጥቂት ቡድኖች የውጭ ምንዛሬን እና የሀገር ውስጥ ብድርን በልዩ ሁኔታ ማግኘት በመቻላቸው ተጠቃሚ መሆናቸውን ጠቁመዋል።
ማልፓስ፤ ስታንሊ ፊሸር መታሰቢያ በተሰኘ መድረክ ላይ ባቀረቡት የፖሊሲ ጥናት ላይ ኢትዮጵያን በዋና ምሳሌነት የተጠቀሙ ሲሆን፥ ሀገሪቱ የእርሻ መሬት፣ የተፈጥሮ ሀብት፣ የውኃ፣ ተስማሚ የአየር ንብረት እና የሰው ኃይል አቅም ያላት በመሆኗ «ትልቅ የእድገት አቅም» ያላት ሀገር እንደሆነች ገልጸዋል።
የዓለም ባንክ በኢትዮጵያ ውስጥ ወደ 200 የሚጠጉ ፕሮጀክቶችን በገንዘብ መደገፉንና 43ቱ አሁንም በሂደት ላይ እንደሚገኙ የጠቆሙት ማልፓስ፤ ሆኖም የሀገሪቱ የነፍስ ወከፍ ገቢ አሁንም 1,100 ዶላር አካባቢ በመሆኑ «ከዓለም ደሃ ሀገራት አንዷ» አድርጓታል ብለዋል።
Seledadotio
Seledadotio
የቀድሞው የዓለም ባንክ ፕሬዝዳንት ዳቪድ ማልፓስ የኢትዮጵያ ብር መዳከም እና የውጭ ምንዛሬ ማሻሻያዎች ድህነትን በከፍተኛ ሁኔታ ማባባሳቸውን በመግለጽ፤ በብር ደመወዝ የሚከፈላቸው ሰዎች «ገቢያቸው እጅግ ቀንሷል» ሲሉ ተናግረዋል።
በተቃራኒው ጥቂት ቡድኖች የውጭ ምንዛሬን እና የሀገር ውስጥ ብድርን በልዩ ሁኔታ ማግኘት በመቻላቸው ተጠቃሚ መሆናቸውን ጠቁመዋል።
ማልፓስ፤ ስታንሊ ፊሸር መታሰቢያ በተሰኘ መድረክ ላይ ባቀረቡት የፖሊሲ ጥናት ላይ ኢትዮጵያን በዋና ምሳሌነት የተጠቀሙ ሲሆን፥ ሀገሪቱ የእርሻ መሬት፣ የተፈጥሮ ሀብት፣ የውኃ፣ ተስማሚ የአየር ንብረት እና የሰው ኃይል አቅም ያላት በመሆኗ «ትልቅ የእድገት አቅም» ያላት ሀገር እንደሆነች ገልጸዋል።
የዓለም ባንክ በኢትዮጵያ ውስጥ ወደ 200 የሚጠጉ ፕሮጀክቶችን በገንዘብ መደገፉንና 43ቱ አሁንም በሂደት ላይ እንደሚገኙ የጠቆሙት ማልፓስ፤ ሆኖም የሀገሪቱ የነፍስ ወከፍ ገቢ አሁንም 1,100 ዶላር አካባቢ በመሆኑ «ከዓለም ደሃ ሀገራት አንዷ» አድርጓታል ብለዋል።
Seledadotio
Seledadotio
3 days ago
የውኃ ሉዓላዊነታችን በተግባር፡ ከ18 ዓመታት የእንቅልፍ ዘመን የነቃው የመገጭ ግድብ
****************
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን ጋር ባደረጉት ቆይታ በአማራ ክልል እየተከናወኑ ያሉ ታላላቅ የልማት ፕሮጀክቶችን በተመለከተ ሰፊ ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡
ከእነዚህ ሀገራዊ ፕሮጀክቶች መካከል የጎንደር ከተማ ነዋሪዎችን የረዥም ዘመን የመጠጥ ውኃ ጥያቄ የሚመልሰው እና ሰፊ የመስኖ ልማት አቅም ያለው የመገጭ ግድብ በግንባር ቀደምትነት ይጠቀሳል፡፡
ግንባታው በ2001 ዓ.ም. የተጀመረው ይህ ግድብ፣ ላለፉት 18 ዓመታት የመልካም አስተዳደር እና የፕሮጀክት አመራር ድክመት ተጓትቶ ቆይቷል፡፡ ይሁን እንጂ በ2017 በጀት ዓመት በጠቅላይ ሚኒስትሩ ቀጥተኛ አመራር፣ አፈጻጸሙ ዝቅተኛ የነበረው ተቋራጭ ከፕሮጀክቱ እንዲወጣ ተደርጎ ሥራው ለሀገር በቀል ተቋራጭ ተሰጥቷል፡፡
የውጭ ከፍተኛ ባለሙያዎች ተጋብዘው የመሬት መንሸራተት ችግሩ በጥናት እንዲፈታ መደረጉ፣ እንዲሁም ሥራው በቀን እና በሌሊት ፈረቃ እንዲከናወን መወሰኑ ፕሮጀክቱን ከእንቅልፉ ቀስቅሶ ወደ ጤናማ እና ፈጣን የአፈጻጸም ምዕራፍ አሸጋግሮታል፡፡
በዚህም የግንባታው ወሳኝ ምዕራፍ የሆነው የወንዝ ቅልበሳ ሙሉ በሙሉ የተጠናቀቀ ሲሆን፣ ፕሮጀክቱ በቅርቡ ለፍሬ እንደሚበቃ ይጠበቃል፡፡
የመገጭ ግድብ ከግንባታ ባለፈ የኢትዮጵያውያን የልማት ፅናት ማሳያ ነው፡፡ አጠቃላይ የውኃ መያዝ አቅሙ 185 ሚሊዮን ኪዩቢክ ሜትር ሲሆን፣ ከዚህ ውስጥ 116 ሚሊዮን ኪዩቢክ ሜትር የሚሆነው ለመስኖ ልማት የሚውል ነው፡፡
ይህም 17 ሺህ ሔክታር መሬትን በመስኖ በማልማት የጎንደር ከተማን እንዲሁም የምሥራቅ እና የምዕራብ ደምቢያ አካባቢ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ ያደርጋል፡፡
ክልሉ ያለውን ሰፊ የውኃ እና የመሬት ሀብት አቀናጅቶ ለመጠቀም እየተገነቡ ካሉ ሰፋፊ የመስኖ አውታሮች አንዱ የሆነው ይህ ፕሮጀክት፣ የሀገራችን የግብርና ትራንስፎርሜሽን እና የምግብ ዋስትና ራዕይ በጉልህ የሚያሳካ የዘመን ትሩፋት ነው፡፡
ይህ የኢትዮጵያ የማይቆም የልማት እርምጃ እንደተለመደው የግብፅ ሚዲያዎችን ሰላም ነስቷል፡፡
የመገጭ ግድብ በጣና ሐይቅ ገባር ወንዝ ላይ የሚገነባ መካከለኛ ፕሮጀክት ቢሆንም፣ የግብፅ ሚዲያዎች ፕሮጀክቱን በተመለከተ ሰሞኑን እያስተጋቡት ያለው ጩኸት ሀገሪቱ ከያዘችው የቆየ እና ራስ ወዳድ የውኃ ፖሊሲ የሚመነጭ ነው፡፡
ግብፅ ኢትዮጵያ የውኃ ሀብቷን እንዳትጠቀም የማስፈራራት ፖሊሲን ብትከተልም፣ ኢትዮጵያ ግን ታላቁን የሕዳሴ ግድብ አጠናቅቃ ልማቷን የሚያፋጥኑ እንደ መገጭ ያሉ ግድቦችን መቀጠ "ኢትዮጵያ አትጨበጥም" የሚል ድንጋጤ ፈጥሮባቸዋል፡፡
ግብፅ አሁንም ጊዜ ያለፈባቸውን የቅኝ ግዛት ውሎች እያነሳች የትኛውም የኢትዮጵያ ልማት ግብርናዋን እንደሚጎዳ በማስመሰል ከእውነት የራቀ ኢ-ፍትሐዊ ትርክት ታራምዳለች፡፡
ኢትዮጵያ ግን ፍትሐዊና ምክንያታዊ የውኃ አጠቃቀም መርህን (CFA) በመከተል ሕዝቧን ለመመገብ የገዛ ሀብቷን የማልማት ተፈጥሯዊና ሕጋዊ መብቷን እያስከበረች ትገኛለች፡፡
ከዚህም ባሻገር እንደ መገጭ ባሉ የኢትዮጵያ ደጋማ ቦታዎች ግድብ መሥራት የውኃ ትነትን እጅግ የሚቀንስ መሆኑ የኢትዮጵያ ልማት ማንንም የማይጎዳ ለመሆኑ ሳይንሳዊ ማረጋገጫ ነው፡፡
እውነታው ኢትዮጵያ አሁን ያለችበት ምዕራፍ ከትላንቱ በእጅጉ የተለየ መሆኑ ነው፡፡ ሀገራችን የዜጎቿን ሕይወት ለመለወጥ እና ከድህነት ለመውጣት የምታደርገውን የልማት ጉዞ በማንኛውም የውጭ ኃይል እጅ ጥምዘዛ የማታቆምበት ታሪካዊ ከፍታ ላይ ትገኛለች፡፡
የመገጭ ግድብም ሆነ ሌሎች በሀገራችን እየተከናወኑ ያሉ የልማት ፕሮጀክቶች የዚሁ ሉዓላዊ መብት አካል ናቸው፡፡
ማንም ይጩህ ማን፣ ኢትዮጵያ በራሷ ሀብት፣ በራሷ አቅም እና በራሷ ጊዜ የጀመረቻቸውን የልማት ሥራዎች ከዳር በማድረስ ታሪኳን በአዲስ መልክ መጻፏን አጠናክራ ትቀጥላለች፡፡
መንግሥትም በቀጣይ የመገጭ ግድብ ቀሪ ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ በማጠናቀቅ፣ የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ሥራዎችን በማጠናከር እና በዓለም አቀፍ ደረጃ የዲፕሎማሲ ሥራውን በማስፋት የኢትዮጵያን ብልጽግና ያረጋግጣል፡፡
በለሚ ታደሰ
#ethiopia #ebc #megechdam #nile #development #amhararegion
****************
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን ጋር ባደረጉት ቆይታ በአማራ ክልል እየተከናወኑ ያሉ ታላላቅ የልማት ፕሮጀክቶችን በተመለከተ ሰፊ ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡
ከእነዚህ ሀገራዊ ፕሮጀክቶች መካከል የጎንደር ከተማ ነዋሪዎችን የረዥም ዘመን የመጠጥ ውኃ ጥያቄ የሚመልሰው እና ሰፊ የመስኖ ልማት አቅም ያለው የመገጭ ግድብ በግንባር ቀደምትነት ይጠቀሳል፡፡
ግንባታው በ2001 ዓ.ም. የተጀመረው ይህ ግድብ፣ ላለፉት 18 ዓመታት የመልካም አስተዳደር እና የፕሮጀክት አመራር ድክመት ተጓትቶ ቆይቷል፡፡ ይሁን እንጂ በ2017 በጀት ዓመት በጠቅላይ ሚኒስትሩ ቀጥተኛ አመራር፣ አፈጻጸሙ ዝቅተኛ የነበረው ተቋራጭ ከፕሮጀክቱ እንዲወጣ ተደርጎ ሥራው ለሀገር በቀል ተቋራጭ ተሰጥቷል፡፡
የውጭ ከፍተኛ ባለሙያዎች ተጋብዘው የመሬት መንሸራተት ችግሩ በጥናት እንዲፈታ መደረጉ፣ እንዲሁም ሥራው በቀን እና በሌሊት ፈረቃ እንዲከናወን መወሰኑ ፕሮጀክቱን ከእንቅልፉ ቀስቅሶ ወደ ጤናማ እና ፈጣን የአፈጻጸም ምዕራፍ አሸጋግሮታል፡፡
በዚህም የግንባታው ወሳኝ ምዕራፍ የሆነው የወንዝ ቅልበሳ ሙሉ በሙሉ የተጠናቀቀ ሲሆን፣ ፕሮጀክቱ በቅርቡ ለፍሬ እንደሚበቃ ይጠበቃል፡፡
የመገጭ ግድብ ከግንባታ ባለፈ የኢትዮጵያውያን የልማት ፅናት ማሳያ ነው፡፡ አጠቃላይ የውኃ መያዝ አቅሙ 185 ሚሊዮን ኪዩቢክ ሜትር ሲሆን፣ ከዚህ ውስጥ 116 ሚሊዮን ኪዩቢክ ሜትር የሚሆነው ለመስኖ ልማት የሚውል ነው፡፡
ይህም 17 ሺህ ሔክታር መሬትን በመስኖ በማልማት የጎንደር ከተማን እንዲሁም የምሥራቅ እና የምዕራብ ደምቢያ አካባቢ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ ያደርጋል፡፡
ክልሉ ያለውን ሰፊ የውኃ እና የመሬት ሀብት አቀናጅቶ ለመጠቀም እየተገነቡ ካሉ ሰፋፊ የመስኖ አውታሮች አንዱ የሆነው ይህ ፕሮጀክት፣ የሀገራችን የግብርና ትራንስፎርሜሽን እና የምግብ ዋስትና ራዕይ በጉልህ የሚያሳካ የዘመን ትሩፋት ነው፡፡
ይህ የኢትዮጵያ የማይቆም የልማት እርምጃ እንደተለመደው የግብፅ ሚዲያዎችን ሰላም ነስቷል፡፡
የመገጭ ግድብ በጣና ሐይቅ ገባር ወንዝ ላይ የሚገነባ መካከለኛ ፕሮጀክት ቢሆንም፣ የግብፅ ሚዲያዎች ፕሮጀክቱን በተመለከተ ሰሞኑን እያስተጋቡት ያለው ጩኸት ሀገሪቱ ከያዘችው የቆየ እና ራስ ወዳድ የውኃ ፖሊሲ የሚመነጭ ነው፡፡
ግብፅ ኢትዮጵያ የውኃ ሀብቷን እንዳትጠቀም የማስፈራራት ፖሊሲን ብትከተልም፣ ኢትዮጵያ ግን ታላቁን የሕዳሴ ግድብ አጠናቅቃ ልማቷን የሚያፋጥኑ እንደ መገጭ ያሉ ግድቦችን መቀጠ "ኢትዮጵያ አትጨበጥም" የሚል ድንጋጤ ፈጥሮባቸዋል፡፡
ግብፅ አሁንም ጊዜ ያለፈባቸውን የቅኝ ግዛት ውሎች እያነሳች የትኛውም የኢትዮጵያ ልማት ግብርናዋን እንደሚጎዳ በማስመሰል ከእውነት የራቀ ኢ-ፍትሐዊ ትርክት ታራምዳለች፡፡
ኢትዮጵያ ግን ፍትሐዊና ምክንያታዊ የውኃ አጠቃቀም መርህን (CFA) በመከተል ሕዝቧን ለመመገብ የገዛ ሀብቷን የማልማት ተፈጥሯዊና ሕጋዊ መብቷን እያስከበረች ትገኛለች፡፡
ከዚህም ባሻገር እንደ መገጭ ባሉ የኢትዮጵያ ደጋማ ቦታዎች ግድብ መሥራት የውኃ ትነትን እጅግ የሚቀንስ መሆኑ የኢትዮጵያ ልማት ማንንም የማይጎዳ ለመሆኑ ሳይንሳዊ ማረጋገጫ ነው፡፡
እውነታው ኢትዮጵያ አሁን ያለችበት ምዕራፍ ከትላንቱ በእጅጉ የተለየ መሆኑ ነው፡፡ ሀገራችን የዜጎቿን ሕይወት ለመለወጥ እና ከድህነት ለመውጣት የምታደርገውን የልማት ጉዞ በማንኛውም የውጭ ኃይል እጅ ጥምዘዛ የማታቆምበት ታሪካዊ ከፍታ ላይ ትገኛለች፡፡
የመገጭ ግድብም ሆነ ሌሎች በሀገራችን እየተከናወኑ ያሉ የልማት ፕሮጀክቶች የዚሁ ሉዓላዊ መብት አካል ናቸው፡፡
ማንም ይጩህ ማን፣ ኢትዮጵያ በራሷ ሀብት፣ በራሷ አቅም እና በራሷ ጊዜ የጀመረቻቸውን የልማት ሥራዎች ከዳር በማድረስ ታሪኳን በአዲስ መልክ መጻፏን አጠናክራ ትቀጥላለች፡፡
መንግሥትም በቀጣይ የመገጭ ግድብ ቀሪ ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ በማጠናቀቅ፣ የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ሥራዎችን በማጠናከር እና በዓለም አቀፍ ደረጃ የዲፕሎማሲ ሥራውን በማስፋት የኢትዮጵያን ብልጽግና ያረጋግጣል፡፡
በለሚ ታደሰ
#ethiopia #ebc #megechdam #nile #development #amhararegion
3 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የኦሮሚያ ክልል ፕሬዝዳንት አቶ ሽመልስ አብዲሳ፣ የክልሉን የደን ሽፋን እና የተፈጥሮ ሀብት እንክብካቤን አስመልክቶ አስገራሚ አሃዞችን ያካተተ መግለጫ ዛሬ አውጥተዋል። ፕሬዝዳንቱ በመግለጫቸው የክልሉ መንግስት አሳክቶታል ያሉትን የአረንጓዴ አሻራ ስኬት ቢያሞካሹም፣ ዘገባው ግን ከመሬት ላይ ካለው እውነታ ጋር የተራራቀ የፖለቲካ ትርክት ነው የሚል ትችት እየቀረበበት ይገኛል።
ባለፉት ሰባት ዓመታት 28 ቢሊዮን ችግኞች መተከላቸውንና 85 በመቶው መጽደቃቸውን የገለጹት አቶ ሽመልስ፣ የክልሉ የደን ሽፋን ከ17 በመቶ ወደ 29 በመቶ ማደጉን ሞግተዋል። ይሁን እንጂ፣ ይህ በመንግስት በኩል ብቻ የቀረበው ግዙፍ አሃዝ በገለልተኛ ሶስተኛ ወገን ያልተረጋገጠ ከመሆኑም በላይ፣ ብዙዎች የችግኝ ተከላ ዘመቻው ከፖለቲካ ፕሮፓጋንዳ ማራመጃነት ባለፈ በተግባር ያመጣው ለውጥ አጠያያቂ መሆኑን ይገልጻሉ።
ፕሬዝዳንቱ በመግለጫቸው የደረቁ ወንዞች ዳግም መንጨታቸውን፣ ራቁታቸውን የነበሩ ተራሮች በደን መሸፈናቸውን፣ የምርት መጠን መጨመሩን እና የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ መቻሉን ተናግረዋል። ነገር ግን መግለጫው ይህንን የተንቆጠቆጠ የልማት እና የብልጽግና ምስል ቢስልም፣ ክልሉ አሁን ካለበት እጅግ አሳሳቢ የጸጥታ መደፍረስ፣ የእርሻ መሬቶች መተው፣ ሰፊ የህዝብ መፈናቀል እና የኑሮ ውድነት አንጻር የቀረበው ሪፖርት የህዝቡን የዕለት ተዕለት ስቃይ የካደ እና እውነታውን የደበቀ ነው ሲሉ የፖለቲካ ተንታኞች ይተቹታል።
ይህ በእንዲህ እንዳለም ሽመልስ የተፈጥሮ ሀብት እንክብካቤውን እንደ ሽፋን በመጠቀም "ኦሮሚያን እንገነባለን፣ ኢትዮጵያን እናጸናለን፣ የአፍሪካ ቀንድንም እናረጋጋለን" የሚል ሰፊ የፖለቲካ መልዕክት ለማስተላለፍ ሞክረዋል። በመጪው ሐምሌ 27 ቀን 2018 ዓ.ም በአንድ ቀን ብቻ 466 ሚሊዮን ችግኞችን እንተክላለን ያሉት ፕሬዝዳንቱ፣ ህዝቡ በነቂስ እንዲወጣ ጥሪ አቅርበዋል።
የአቶ ሽመልስ አብዲሳ መግለጫ የአካባቢ ጥበቃን ሽፋን ያደረገ ቢመስልም፣ በውስጡ ግን የክልሉ መንግስት ያለበትን ከፍተኛ የጸጥታና አስተዳደራዊ ውድቀቶች በመሸፈን፣ የፖለቲካ ቅቡልነትን ለማግኘት እና ህዝቡን በልማት ስም ለማስተባበር የተሞከረበት ፖለቲካዊ ቅስቀሳ መሆኑን የፖለቲካ ታዛቢዎች ያነሳሉ። መሬት ላይ ያለው ማህበራዊ እና ፖለቲካዊ ቀውስ ሳይፈታ፣ በቢሊዮኖች የሚቆጠሩ ችግኞችን ተክለናል የሚለው ትርክት የክልሉን መሰረታዊ ችግሮች ሊፈታው እንደማይችልም አበክረው ይገልጻሉ።
ባለፉት ሰባት ዓመታት 28 ቢሊዮን ችግኞች መተከላቸውንና 85 በመቶው መጽደቃቸውን የገለጹት አቶ ሽመልስ፣ የክልሉ የደን ሽፋን ከ17 በመቶ ወደ 29 በመቶ ማደጉን ሞግተዋል። ይሁን እንጂ፣ ይህ በመንግስት በኩል ብቻ የቀረበው ግዙፍ አሃዝ በገለልተኛ ሶስተኛ ወገን ያልተረጋገጠ ከመሆኑም በላይ፣ ብዙዎች የችግኝ ተከላ ዘመቻው ከፖለቲካ ፕሮፓጋንዳ ማራመጃነት ባለፈ በተግባር ያመጣው ለውጥ አጠያያቂ መሆኑን ይገልጻሉ።
ፕሬዝዳንቱ በመግለጫቸው የደረቁ ወንዞች ዳግም መንጨታቸውን፣ ራቁታቸውን የነበሩ ተራሮች በደን መሸፈናቸውን፣ የምርት መጠን መጨመሩን እና የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ መቻሉን ተናግረዋል። ነገር ግን መግለጫው ይህንን የተንቆጠቆጠ የልማት እና የብልጽግና ምስል ቢስልም፣ ክልሉ አሁን ካለበት እጅግ አሳሳቢ የጸጥታ መደፍረስ፣ የእርሻ መሬቶች መተው፣ ሰፊ የህዝብ መፈናቀል እና የኑሮ ውድነት አንጻር የቀረበው ሪፖርት የህዝቡን የዕለት ተዕለት ስቃይ የካደ እና እውነታውን የደበቀ ነው ሲሉ የፖለቲካ ተንታኞች ይተቹታል።
ይህ በእንዲህ እንዳለም ሽመልስ የተፈጥሮ ሀብት እንክብካቤውን እንደ ሽፋን በመጠቀም "ኦሮሚያን እንገነባለን፣ ኢትዮጵያን እናጸናለን፣ የአፍሪካ ቀንድንም እናረጋጋለን" የሚል ሰፊ የፖለቲካ መልዕክት ለማስተላለፍ ሞክረዋል። በመጪው ሐምሌ 27 ቀን 2018 ዓ.ም በአንድ ቀን ብቻ 466 ሚሊዮን ችግኞችን እንተክላለን ያሉት ፕሬዝዳንቱ፣ ህዝቡ በነቂስ እንዲወጣ ጥሪ አቅርበዋል።
የአቶ ሽመልስ አብዲሳ መግለጫ የአካባቢ ጥበቃን ሽፋን ያደረገ ቢመስልም፣ በውስጡ ግን የክልሉ መንግስት ያለበትን ከፍተኛ የጸጥታና አስተዳደራዊ ውድቀቶች በመሸፈን፣ የፖለቲካ ቅቡልነትን ለማግኘት እና ህዝቡን በልማት ስም ለማስተባበር የተሞከረበት ፖለቲካዊ ቅስቀሳ መሆኑን የፖለቲካ ታዛቢዎች ያነሳሉ። መሬት ላይ ያለው ማህበራዊ እና ፖለቲካዊ ቀውስ ሳይፈታ፣ በቢሊዮኖች የሚቆጠሩ ችግኞችን ተክለናል የሚለው ትርክት የክልሉን መሰረታዊ ችግሮች ሊፈታው እንደማይችልም አበክረው ይገልጻሉ።
3 days ago
ታይላንድን እንዳየኋት፤ የ"Destination" ሳይሆን የ"Experience Economy" አገር
የጉዞ ማስታወሻ | በገብረማሪያም ይርጋ
#ethiopia | በዓለም የቱሪዝም ካርታ ላይ ታይላንድ በብዙ ጊዜ እንደ ውብ መዳረሻ ትጠቀሳለች። ነገር ግን አገሪቱን በቅርብ ለሚመለከት ሰው የሚታየው ከውብ ዳርቻዎች፣ ከቤተመቅደሶች ወይም ከሌሊት ሕይወቷ በላይ የሆነ እውነታ አለ፤ ታይላንድ ቱሪዝምን እንደ "ልምድ" በመሸጥ ኢኮኖሚዋን የምታንቀሳቅስ አገር ሆናለች።
የተባበሩት መንግስታት የቱሪዝም ድርጅት (UN Tourism) እና የዓለም ጉዞና ቱሪዝም ካውንስል (WTTC) እንደሚገልጹት፣ ታይላንድ በዓለም ከፍተኛ የቱሪስት ፍሰት ከሚያስተናግዱ አገራት መካከል ትገኛለች፤ ይህም የሆነው ተፈጥሮ ሀብቷ ብቻ ሳይሆን በተቀናጀ የልምድ ኢኮኖሚ ስርዓቷ ምክንያት ነው።
ቱሪዝም ማለት ቦታ ሳይሆን ልምድ ነው
ዛሬ ዓለም አቀፍ የቱሪዝም ገበያ ተቀይሯል። ተጓዦች "ምን አየሁ?" ከማለት ይልቅ "ምን አጋጠመኝ?" ብለው የሚያስታውሱትን ጉዞ ይፈልጋሉ።
በባንኮክ የጎዳና ምግብ ማጣጣም፣ በቺያንግ ማይ የባህል በዓል መካፈል፣ በፉኬት የባሕር ስፖርት መሞከር፣ የታይ ማሳጅና የWellness አገልግሎት መውሰድ፣ የምሽት ገበያዎችን መጎብኘት፤ እነዚህ ሁሉ ተጣምረው የሚሸጠው "ታይላንድ" የተባለውን ልምድ ነው።
የሀብት እሴት በአቀራረብ ይወሰናል
ታይላንድ ያላትን ቅርስ እና ተፈጥሮ በሙያዊ የመዳረሻ አስተዳደር፣ በጠንካራ ብራንዲንግ፣ በዲጂታል ግብይት፣ በጥራት አገልግሎት እና በማህበረሰብ ተሳትፎ አዋህዳ የዓለም ገበያ ምርት አድርጋዋለች።
ይህ ትምህርት ለኢትዮጵያም ትልቅ መልዕክት አለው።
ኢትዮጵያ ያላት ሀብት ከብዙዎች ይበልጣል
የሰው ልጅ መገኛ ታሪክ፣ የዓለም ቅርሶች፣ የተራሮች ውበት፣ የባህል ልዩነት፣ የቡና ታሪክ፣ ሃይማኖታዊ ቅርሶች፣ የዱር እንስሳት፣ ባህላዊ ምግቦች እና የሙዚቃ ቅርስ፤ እነዚህ ሁሉ በአንድ አገር ውስጥ የተሰበሰቡ የቱሪዝም ሀብቶች ናቸው።
ስለዚህ የወደፊቱ ጥያቄ "ምን አለን?" መሆን የለበትም። "ዓለም ሌላ ቦታ ማያገኘውን ምን ዓይነት ልምድ እንፈጥራለን?" መሆን አለበት።
የወደፊቱ አቅጣጫ
ዓለም አቀፍ ተሞክሮዎች እንደሚያሳዩት የቱሪዝም ስኬት በአምስት ዋና መሠረቶች ላይ ይቆማል፦
ዘመናዊ የመዳረሻ አስተዳደር (Destination Management)
የማይረሳ የቱሪስት ልምድ ንድፍ (Experience Design)
ለተለያዩ የዓለም ገበያዎች የተለየ የብራንድ እና የግብይት ስትራቴጂ
የቱሪዝም ገቢ ለአካባቢ ማህበረሰቦች የሚደርስበት የእሴት ሰንሰለት
በመረጃ የሚመራ የቱሪዝም እቅድና ውሳኔ
መደምደሚያ
ታይላንድ የሰጠችኝ ትልቁ ትምህርት አንድ ነው፤ ቱሪዝም በመስህብ ብዛት አይለካም፣ በተጓዦች ልብ ውስጥ በሚቀር ልምድ ይለካል።
ኢትዮጵያ የሌሎችን ሞዴል መቅዳት አያስፈልጋትም። የራሷን ታሪክ፣ ባህል፣ ተፈጥሮ እና ማንነት በዘመናዊ አቀራረብ ወደ ዓለም ገበያ ማቅረብ ብቻ ይበቃታል።
የወደፊቱ የቱሪዝም ውድድር በተፈጥሮ ሀብት ብቻ አይወሰንም፤ ሀብትን ወደ ምርት → ልምድ → ብራንድ → ገበያ → ዘላቂ ኢኮኖሚ የመቀየር ብቃት ይወስነዋል።
እናም ዛሬ ኢትዮጵያ ራሷን ልትጠይቅ የሚገባት አንድ ጥያቄ ብቻ ነው፦
"ዓለም ሌላ ቦታ ፈጽሞ ማያገኘውን ምን ዓይነት ልምድ በኢትዮጵያ ብቻ ማቅረብ እንችላለን?"
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
የጉዞ ማስታወሻ | በገብረማሪያም ይርጋ
#ethiopia | በዓለም የቱሪዝም ካርታ ላይ ታይላንድ በብዙ ጊዜ እንደ ውብ መዳረሻ ትጠቀሳለች። ነገር ግን አገሪቱን በቅርብ ለሚመለከት ሰው የሚታየው ከውብ ዳርቻዎች፣ ከቤተመቅደሶች ወይም ከሌሊት ሕይወቷ በላይ የሆነ እውነታ አለ፤ ታይላንድ ቱሪዝምን እንደ "ልምድ" በመሸጥ ኢኮኖሚዋን የምታንቀሳቅስ አገር ሆናለች።
የተባበሩት መንግስታት የቱሪዝም ድርጅት (UN Tourism) እና የዓለም ጉዞና ቱሪዝም ካውንስል (WTTC) እንደሚገልጹት፣ ታይላንድ በዓለም ከፍተኛ የቱሪስት ፍሰት ከሚያስተናግዱ አገራት መካከል ትገኛለች፤ ይህም የሆነው ተፈጥሮ ሀብቷ ብቻ ሳይሆን በተቀናጀ የልምድ ኢኮኖሚ ስርዓቷ ምክንያት ነው።
ቱሪዝም ማለት ቦታ ሳይሆን ልምድ ነው
ዛሬ ዓለም አቀፍ የቱሪዝም ገበያ ተቀይሯል። ተጓዦች "ምን አየሁ?" ከማለት ይልቅ "ምን አጋጠመኝ?" ብለው የሚያስታውሱትን ጉዞ ይፈልጋሉ።
በባንኮክ የጎዳና ምግብ ማጣጣም፣ በቺያንግ ማይ የባህል በዓል መካፈል፣ በፉኬት የባሕር ስፖርት መሞከር፣ የታይ ማሳጅና የWellness አገልግሎት መውሰድ፣ የምሽት ገበያዎችን መጎብኘት፤ እነዚህ ሁሉ ተጣምረው የሚሸጠው "ታይላንድ" የተባለውን ልምድ ነው።
የሀብት እሴት በአቀራረብ ይወሰናል
ታይላንድ ያላትን ቅርስ እና ተፈጥሮ በሙያዊ የመዳረሻ አስተዳደር፣ በጠንካራ ብራንዲንግ፣ በዲጂታል ግብይት፣ በጥራት አገልግሎት እና በማህበረሰብ ተሳትፎ አዋህዳ የዓለም ገበያ ምርት አድርጋዋለች።
ይህ ትምህርት ለኢትዮጵያም ትልቅ መልዕክት አለው።
ኢትዮጵያ ያላት ሀብት ከብዙዎች ይበልጣል
የሰው ልጅ መገኛ ታሪክ፣ የዓለም ቅርሶች፣ የተራሮች ውበት፣ የባህል ልዩነት፣ የቡና ታሪክ፣ ሃይማኖታዊ ቅርሶች፣ የዱር እንስሳት፣ ባህላዊ ምግቦች እና የሙዚቃ ቅርስ፤ እነዚህ ሁሉ በአንድ አገር ውስጥ የተሰበሰቡ የቱሪዝም ሀብቶች ናቸው።
ስለዚህ የወደፊቱ ጥያቄ "ምን አለን?" መሆን የለበትም። "ዓለም ሌላ ቦታ ማያገኘውን ምን ዓይነት ልምድ እንፈጥራለን?" መሆን አለበት።
የወደፊቱ አቅጣጫ
ዓለም አቀፍ ተሞክሮዎች እንደሚያሳዩት የቱሪዝም ስኬት በአምስት ዋና መሠረቶች ላይ ይቆማል፦
ዘመናዊ የመዳረሻ አስተዳደር (Destination Management)
የማይረሳ የቱሪስት ልምድ ንድፍ (Experience Design)
ለተለያዩ የዓለም ገበያዎች የተለየ የብራንድ እና የግብይት ስትራቴጂ
የቱሪዝም ገቢ ለአካባቢ ማህበረሰቦች የሚደርስበት የእሴት ሰንሰለት
በመረጃ የሚመራ የቱሪዝም እቅድና ውሳኔ
መደምደሚያ
ታይላንድ የሰጠችኝ ትልቁ ትምህርት አንድ ነው፤ ቱሪዝም በመስህብ ብዛት አይለካም፣ በተጓዦች ልብ ውስጥ በሚቀር ልምድ ይለካል።
ኢትዮጵያ የሌሎችን ሞዴል መቅዳት አያስፈልጋትም። የራሷን ታሪክ፣ ባህል፣ ተፈጥሮ እና ማንነት በዘመናዊ አቀራረብ ወደ ዓለም ገበያ ማቅረብ ብቻ ይበቃታል።
የወደፊቱ የቱሪዝም ውድድር በተፈጥሮ ሀብት ብቻ አይወሰንም፤ ሀብትን ወደ ምርት → ልምድ → ብራንድ → ገበያ → ዘላቂ ኢኮኖሚ የመቀየር ብቃት ይወስነዋል።
እናም ዛሬ ኢትዮጵያ ራሷን ልትጠይቅ የሚገባት አንድ ጥያቄ ብቻ ነው፦
"ዓለም ሌላ ቦታ ፈጽሞ ማያገኘውን ምን ዓይነት ልምድ በኢትዮጵያ ብቻ ማቅረብ እንችላለን?"
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
Sponsored by
Surafel
4 days ago
“በብር ደመወዝ የሚከፈላቸው ሰዎች ገቢያቸው እጅግ ቀንሷል”፦ የቀድሞው የዓለም ባንክ ፕሬዝዳንት የ #ኢትዮጵያ የምንዛሬ ሪፎርም ድህነትን አባብሷል አሉ
የቀድሞው የዓለም ባንክ ፕሬዝዳንት ዴቪድ ማልፓስ የኢትዮጵያ ብር መዳከም እና የውጭ ምንዛሬ ማሻሻያዎች ድህነትን በከፍተኛ ሁኔታ ማባባሳቸውን በመግለጽ፤ በብር ደመወዝ የሚከፈላቸው ሰዎች «ገቢያቸው እጅግ ቀንሷል» ሲሉ ተናግረዋል። በተቃራኒው ጥቂት ቡድኖች የውጭ ምንዛሬን እና የሀገር ውስጥ ብድርን በልዩ ሁኔታ ማግኘት በመቻላቸው ተጠቃሚ መሆናቸውን ጠቁመዋል።
ማልፓስ፤ ስታንሊ ፊሸር መታሰቢያ በተሰኘ መድረክ ላይ ባቀረቡት የፖሊሲ ጥናት ላይ ኢትዮጵያን በዋና ምሳሌነት የተጠቀሙ ሲሆን፥ ሀገሪቱ የእርሻ መሬት፣ የተፈጥሮ ሀብት፣ የውኃ፣ ተስማሚ የአየር ንብረት እና የሰው ኃይል አቅም ያላት በመሆኗ «ትልቅ የእድገት አቅም» ያላት ሀገር እንደሆነች ገልጸዋል።
የዓለም ባንክ በኢትዮጵያ ውስጥ ወደ 200 የሚጠጉ ፕሮጀክቶችን በገንዘብ መደገፉንና 43ቱ አሁንም በሂደት ላይ እንደሚገኙ የጠቆሙት ማልፓስ፤ ሆኖም የሀገሪቱ የነፍስ ወከፍ ገቢ አሁንም 1,100 ዶላር አካባቢ በመሆኑ «ከዓለም ደሃ ሀገራት አንዷ» አድርጓታል ብለዋል።
Seledadotio
Seledadotio
የቀድሞው የዓለም ባንክ ፕሬዝዳንት ዴቪድ ማልፓስ የኢትዮጵያ ብር መዳከም እና የውጭ ምንዛሬ ማሻሻያዎች ድህነትን በከፍተኛ ሁኔታ ማባባሳቸውን በመግለጽ፤ በብር ደመወዝ የሚከፈላቸው ሰዎች «ገቢያቸው እጅግ ቀንሷል» ሲሉ ተናግረዋል። በተቃራኒው ጥቂት ቡድኖች የውጭ ምንዛሬን እና የሀገር ውስጥ ብድርን በልዩ ሁኔታ ማግኘት በመቻላቸው ተጠቃሚ መሆናቸውን ጠቁመዋል።
ማልፓስ፤ ስታንሊ ፊሸር መታሰቢያ በተሰኘ መድረክ ላይ ባቀረቡት የፖሊሲ ጥናት ላይ ኢትዮጵያን በዋና ምሳሌነት የተጠቀሙ ሲሆን፥ ሀገሪቱ የእርሻ መሬት፣ የተፈጥሮ ሀብት፣ የውኃ፣ ተስማሚ የአየር ንብረት እና የሰው ኃይል አቅም ያላት በመሆኗ «ትልቅ የእድገት አቅም» ያላት ሀገር እንደሆነች ገልጸዋል።
የዓለም ባንክ በኢትዮጵያ ውስጥ ወደ 200 የሚጠጉ ፕሮጀክቶችን በገንዘብ መደገፉንና 43ቱ አሁንም በሂደት ላይ እንደሚገኙ የጠቆሙት ማልፓስ፤ ሆኖም የሀገሪቱ የነፍስ ወከፍ ገቢ አሁንም 1,100 ዶላር አካባቢ በመሆኑ «ከዓለም ደሃ ሀገራት አንዷ» አድርጓታል ብለዋል።
Seledadotio
Seledadotio
4 days ago
"ኮከል ማሚቶ" : በካፋ ባህል ላይ የሚያተኩር የኢትኖግራፊ መጽሐፍ በቦንጋ ነገ ይመረቃል
#ethiopia | በካፋ ባህል፣ ታሪክ እና የማህበረሰቡ የኑሮ ዘይቤ ላይ የሚያተኩረው "ኮከል ማሚቶ" የተሰኘ የኢትኖግራፊ መጽሐፍ እሁድ፣ ሐምሌ 26 / 2018ዓ.ም ከቀኑ 8:00 ሰዓት በቦንጋ ከተማ በICT አዳራሽ በይፋ ይመረቃል።
መጽሐፉ በአምስት ዋና ዋና ክፍሎች የተደራጀ ሲሆን፣ የካፋን ማህበረሰብ ከሙዚቃ፣ ከመናፍስት እምነቶች፣ ከጦረኝነት ባህል፣ ከተፈጥሮ ጋር ካለው ትስስር እንዲሁም ከአዕዋፋት ጋር የተያያዙ በርካታ ባህላዊና ማህበራዊ ጉዳዮችን በሰፊው ይዳስሳል።
በባህል፣ በማህበረሰብ እና በነባር የኑሮ ትስስር ላይ የሚያተኩሩ የኢትኖግራፊ ሥራዎች በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ እምብዛም በማይገኙበት ሁኔታ፣ "ኮከል ማሚቶ" በዘርፉ አዲስ አቅጣጫ የሚከፍት እና ለቀጣይ የምርምርና የጽሑፍ ሥራዎች መነሻ የሚሆን መጽሐፍ እንደሚሆን ተስፋ ተጥሎበታል።
የመጽሐፉ ምረቃ ሥነ ሥርዓት የባህል ባለሙያዎችን፣ የሥነ ጽሑፍ ወዳጆችን፣ ተመራማሪዎችን እና የካፋ ባህልን ለማወቅ ፍላጎት ያላቸውን ሁሉ እንዲታደሙ ጥሪ ያቀርባል።
#ethiopia | በካፋ ባህል፣ ታሪክ እና የማህበረሰቡ የኑሮ ዘይቤ ላይ የሚያተኩረው "ኮከል ማሚቶ" የተሰኘ የኢትኖግራፊ መጽሐፍ እሁድ፣ ሐምሌ 26 / 2018ዓ.ም ከቀኑ 8:00 ሰዓት በቦንጋ ከተማ በICT አዳራሽ በይፋ ይመረቃል።
መጽሐፉ በአምስት ዋና ዋና ክፍሎች የተደራጀ ሲሆን፣ የካፋን ማህበረሰብ ከሙዚቃ፣ ከመናፍስት እምነቶች፣ ከጦረኝነት ባህል፣ ከተፈጥሮ ጋር ካለው ትስስር እንዲሁም ከአዕዋፋት ጋር የተያያዙ በርካታ ባህላዊና ማህበራዊ ጉዳዮችን በሰፊው ይዳስሳል።
በባህል፣ በማህበረሰብ እና በነባር የኑሮ ትስስር ላይ የሚያተኩሩ የኢትኖግራፊ ሥራዎች በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ እምብዛም በማይገኙበት ሁኔታ፣ "ኮከል ማሚቶ" በዘርፉ አዲስ አቅጣጫ የሚከፍት እና ለቀጣይ የምርምርና የጽሑፍ ሥራዎች መነሻ የሚሆን መጽሐፍ እንደሚሆን ተስፋ ተጥሎበታል።
የመጽሐፉ ምረቃ ሥነ ሥርዓት የባህል ባለሙያዎችን፣ የሥነ ጽሑፍ ወዳጆችን፣ ተመራማሪዎችን እና የካፋ ባህልን ለማወቅ ፍላጎት ያላቸውን ሁሉ እንዲታደሙ ጥሪ ያቀርባል።
4 days ago
800 ሚሊዮን ችግኞች በአንድ ጀምበር ኢትዮጵያ ለዓለም የምታሳየው ታሪካዊ የአረንጓዴ አሻራ
************************
ኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥ የሚያስከትለውን ዘመነ-ተሻጋሪ ተጽዕኖ ለመቋቋም፣ የተጎዱ መሬቶችን ለማደስ እና የዜጎችን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ህይወት ለማሻሻል ያለመ ሀገራዊ ራዕይ ሰንቃ በመንቀሳቀስ ላይ ትገኛለች።
የዚሁ ዘላቂ ጥረት አካል የሆነውና በአንድ ጀምበር 800 ሚሊዮን ችግኞችን ለመትከል የተያዘው ግብ፣ ሀገራችን ለአረንጓዴ ልማትና ለአካባቢ ጥበቃ ያላትን ጽኑ ቁርጠኝነት ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ዳግም በተግባር የሚያስመሰክር ታሪካዊ ምዕራፍ ነው።
ይህ ዘመቻ ተራ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ብቻ ሳይሆን፣ ከጫፍ እስከ ጫፍ በመላው ኢትዮጵያ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች በአንድ ልብና በአንድ ዓላማ በመነሳት የሚያደርጉት የተቀናጀ አቅምና አንድነት ማሳያ እንዲሁም የተፈጥሮ ሚዛንን ለመመለስ የተደረገ ትልቅ ሀገራዊ ንቅናቄ ነው።
በዚህ ታሪካዊ ቀን ከሚተከሉት ችግኞች መካከል ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው እንደ አቮካዶ፣ ማንጎ፣ ፓፓያ እና ዘይቱን ያሉ ለምግብነት የሚውሉ የፍራፍሬ ተክሎች ይገኙበታል።
እነዚህ የፍራፍሬ ዛፎች የምግብ አቅርቦትን ከማሳደግ ባሻገር ለገበሬዎች የገቢ ምንጭ በመሆን የገጠር ኢኮኖሚን ለማጠናከር በከፍተኛ ሁኔታ ያግዛሉ።
በተጨማሪም የደን ሽፋን መጨመር የአፈር መሸርሸርን ከመከላከል ባለፈ የከርሰ ምድር ውሃ እንዲጎለብት ያደርጋል፤ ታላላቅ የኃይል ማመንጫ ግድቦች እና የመስኖ መሠረተ ልማቶች በደለል እንዳይሞሉ በመከላከል የአገልግሎት ዘመናቸውን ያራዝማል።
የአካባቢ ሙቀትን በመቀነስና የዝናብ ዘይቤን በማስተካከልም ለግብርናው ዘርፍ የተሻለ እና አስተማማኝ ሁኔታ ይፈጥራል።
የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የነገዋን አረንጓዴ፣ በምግብ ራሷን የቻለች እና የተፈጥሮ ሀብቷ የተጠበቀ ኢትዮጵያን ለመገንባት የተጣለ ጠንካራ መሠረት ነው።
ዛሬ በትጋት መሬት የሚይዘው እያንዳንዱ ችግኝ የነገው የኢትዮጵያ ብሩህ ተስፋ፣ አረንጓዴ ተፈጥሮ እና ለቀጣዩ ትውልድ የሚተላለፍ ታሪካዊ አሻራ ደማቅ መገለጫ ነው።
በኢንቲሃድ አብራር
#greenlegacy #ethiopia #climateaction #treeplanting #sustainability
************************
ኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥ የሚያስከትለውን ዘመነ-ተሻጋሪ ተጽዕኖ ለመቋቋም፣ የተጎዱ መሬቶችን ለማደስ እና የዜጎችን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ህይወት ለማሻሻል ያለመ ሀገራዊ ራዕይ ሰንቃ በመንቀሳቀስ ላይ ትገኛለች።
የዚሁ ዘላቂ ጥረት አካል የሆነውና በአንድ ጀምበር 800 ሚሊዮን ችግኞችን ለመትከል የተያዘው ግብ፣ ሀገራችን ለአረንጓዴ ልማትና ለአካባቢ ጥበቃ ያላትን ጽኑ ቁርጠኝነት ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ዳግም በተግባር የሚያስመሰክር ታሪካዊ ምዕራፍ ነው።
ይህ ዘመቻ ተራ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ብቻ ሳይሆን፣ ከጫፍ እስከ ጫፍ በመላው ኢትዮጵያ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች በአንድ ልብና በአንድ ዓላማ በመነሳት የሚያደርጉት የተቀናጀ አቅምና አንድነት ማሳያ እንዲሁም የተፈጥሮ ሚዛንን ለመመለስ የተደረገ ትልቅ ሀገራዊ ንቅናቄ ነው።
በዚህ ታሪካዊ ቀን ከሚተከሉት ችግኞች መካከል ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው እንደ አቮካዶ፣ ማንጎ፣ ፓፓያ እና ዘይቱን ያሉ ለምግብነት የሚውሉ የፍራፍሬ ተክሎች ይገኙበታል።
እነዚህ የፍራፍሬ ዛፎች የምግብ አቅርቦትን ከማሳደግ ባሻገር ለገበሬዎች የገቢ ምንጭ በመሆን የገጠር ኢኮኖሚን ለማጠናከር በከፍተኛ ሁኔታ ያግዛሉ።
በተጨማሪም የደን ሽፋን መጨመር የአፈር መሸርሸርን ከመከላከል ባለፈ የከርሰ ምድር ውሃ እንዲጎለብት ያደርጋል፤ ታላላቅ የኃይል ማመንጫ ግድቦች እና የመስኖ መሠረተ ልማቶች በደለል እንዳይሞሉ በመከላከል የአገልግሎት ዘመናቸውን ያራዝማል።
የአካባቢ ሙቀትን በመቀነስና የዝናብ ዘይቤን በማስተካከልም ለግብርናው ዘርፍ የተሻለ እና አስተማማኝ ሁኔታ ይፈጥራል።
የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የነገዋን አረንጓዴ፣ በምግብ ራሷን የቻለች እና የተፈጥሮ ሀብቷ የተጠበቀ ኢትዮጵያን ለመገንባት የተጣለ ጠንካራ መሠረት ነው።
ዛሬ በትጋት መሬት የሚይዘው እያንዳንዱ ችግኝ የነገው የኢትዮጵያ ብሩህ ተስፋ፣ አረንጓዴ ተፈጥሮ እና ለቀጣዩ ትውልድ የሚተላለፍ ታሪካዊ አሻራ ደማቅ መገለጫ ነው።
በኢንቲሃድ አብራር
#greenlegacy #ethiopia #climateaction #treeplanting #sustainability
4 days ago
መሣሪያን በብዕር የተኩ እጆች፤ የሀገራዊ ምክክር ታሪካዊ ምዕራፍ
***************
የግጭትን መንገድ ትቶ ወደ ሰላማዊ ውይይት በመምጣት በአንድ መድረክ ላይ በእጃቸው መሳሪያ ሳይሆን ብዕርን በመያዝ ሀሳባቸውን ለማስፈር መላው ኢትዮጵያውያን ተገናኝተዋል።
የሀገር ግንባታ መሠረቱ የሚጠነክረው በግጭት ሳይሆን በመደማመጥ፣ እንዲሁም በጋራ በሚገነባ የሀሳብ ራዕይ መሆኑን በማስረፅ።
በዚህ እሳቤ መሠረት ነው የሀገራዊ ምክክር ሂደት "የሁሉም ሀሳብ ለኢትዮጵያ ያስፈልጋል" በሚል መርህ የሁሉንም ድምፅ ለማዳመጥ በር የከፈተው።
ሀገራዊ ምክክር ዓላማው ልክ እንደ ውድድር አሸናፊና ተሸናፊ መለየት ሳይሆን በሕዝቦች ዘንድ የተወከሉ ተወካዮች ተጠናክረው የጋራ መፍትሔ በመፈለግ በሁሉም ውስጥ ኢትዮጵያን አሸናፊ ማድረግ ነው።
ለዚህም ዋና ማሳያ የሆነው ከ4 ሺህ በላይ ተመካካሪዎች በስምንት ዋና ዋና ሀገራዊ አጀንዳዎች ዙሪያ ከመላው ኢትዮጵያ የተወከሉ በቡድን ተከፋፍለው እየተወያዩ ይገኛሉ።
ዓመታትን በትጥቅ ትግል ያሳለፉ ተመካካሪዎች ዛሬ መሣሪያን አስቀምጠው ብዕር በመያዝ ሐሳባቸውን በውይይት እያቀረቡ ይገኛሉ፤ ይህ የሚጠቁመው ምልክት የጦርነትን ኃይል ሳይሆን በመመካከር ችግሮች ሊፈቱ እንደሚችሉ የሚያሳይ ተስፋ ሰጪ ምልክት እና የሰላም መንገድ ለሁሉም ክፍት መሆኑን ያረጋግጣል።
ተመካካሪዎቹ ከ250 አባላት ወደ 50 አባላት፣ በመጨረሻም ወደ 10 አባላት በመከፋፈል ሁሉም ተመካካሪ ያመጣውን የማኅበረሰብ ጥያቄና ሐሳብ ያለ ግፊት፣ ያለ ፍርሃት እና ያለ ተፅዕኖ በነፃነት እንዲያቀርብ ዕድል ተፈጥሮለታል።
ልዩነታቸው ውበታቸው የሆነው የኢትዮጵያውያን ሐሳቦች ሲገናኙ፣ ልዩነቶች ሲከበሩ እና ሁሉም ድምፅ የመደመጥ ዕድል ሲያገኝ፣ የነገዋ ኢትዮጵያ በተስፋ እና በመተማመን የተመሠረተች ትሆናለች። ለዘመናት የቆዩ ቁርሾዎችን በጠረጴዛ ዙሪያ በመፍታት የሰላም ባህልን ማጠናከር የዚህ ሂደት ትልቁ ስኬት ነው።
በዚህ መድረክ ላይ የሚጻፉት ቃላት በወረቀት ላይ ብቻ አይቀሩም፤ ወደ ታሪክ በመሻገር ከአዳራሹ አልፈው የቀጣዮቹን ትውልዶች ሊመሩ የሚችሉ እና ተስፋን፣ ይቅርታን፣ የጋራ ራዕይን የሚተክሉ ናቸው።
በዚህም ሀገር የምትገነባው በዜጎቿ የተረጋጋ ውይይት በመሆኑ ወደ ምክክር መምጣት የድክመት ምልክት ሳይሆን የብስለት፣ የኃላፊነት እና የጋራ የወደፊት ዕጣ ፈንታን በሰላማዊ መንገድ ለመወሰን የተወሰደ ጠንካራ እርምጃ ነው።
መሣሪያን በብዕር የተኩ እጆች የሚጽፉት የአንድ ቡድን ታሪክ አይደለም፤ የሁሉም ኢትዮጵያውያን የጋራ የወደፊት ምዕራፍን ነው።
በልዩ እሸቱ
#nationaldialogue #peacebuilding #futureethiopia #inclusion #unityindiversity #reconciliation
***************
የግጭትን መንገድ ትቶ ወደ ሰላማዊ ውይይት በመምጣት በአንድ መድረክ ላይ በእጃቸው መሳሪያ ሳይሆን ብዕርን በመያዝ ሀሳባቸውን ለማስፈር መላው ኢትዮጵያውያን ተገናኝተዋል።
የሀገር ግንባታ መሠረቱ የሚጠነክረው በግጭት ሳይሆን በመደማመጥ፣ እንዲሁም በጋራ በሚገነባ የሀሳብ ራዕይ መሆኑን በማስረፅ።
በዚህ እሳቤ መሠረት ነው የሀገራዊ ምክክር ሂደት "የሁሉም ሀሳብ ለኢትዮጵያ ያስፈልጋል" በሚል መርህ የሁሉንም ድምፅ ለማዳመጥ በር የከፈተው።
ሀገራዊ ምክክር ዓላማው ልክ እንደ ውድድር አሸናፊና ተሸናፊ መለየት ሳይሆን በሕዝቦች ዘንድ የተወከሉ ተወካዮች ተጠናክረው የጋራ መፍትሔ በመፈለግ በሁሉም ውስጥ ኢትዮጵያን አሸናፊ ማድረግ ነው።
ለዚህም ዋና ማሳያ የሆነው ከ4 ሺህ በላይ ተመካካሪዎች በስምንት ዋና ዋና ሀገራዊ አጀንዳዎች ዙሪያ ከመላው ኢትዮጵያ የተወከሉ በቡድን ተከፋፍለው እየተወያዩ ይገኛሉ።
ዓመታትን በትጥቅ ትግል ያሳለፉ ተመካካሪዎች ዛሬ መሣሪያን አስቀምጠው ብዕር በመያዝ ሐሳባቸውን በውይይት እያቀረቡ ይገኛሉ፤ ይህ የሚጠቁመው ምልክት የጦርነትን ኃይል ሳይሆን በመመካከር ችግሮች ሊፈቱ እንደሚችሉ የሚያሳይ ተስፋ ሰጪ ምልክት እና የሰላም መንገድ ለሁሉም ክፍት መሆኑን ያረጋግጣል።
ተመካካሪዎቹ ከ250 አባላት ወደ 50 አባላት፣ በመጨረሻም ወደ 10 አባላት በመከፋፈል ሁሉም ተመካካሪ ያመጣውን የማኅበረሰብ ጥያቄና ሐሳብ ያለ ግፊት፣ ያለ ፍርሃት እና ያለ ተፅዕኖ በነፃነት እንዲያቀርብ ዕድል ተፈጥሮለታል።
ልዩነታቸው ውበታቸው የሆነው የኢትዮጵያውያን ሐሳቦች ሲገናኙ፣ ልዩነቶች ሲከበሩ እና ሁሉም ድምፅ የመደመጥ ዕድል ሲያገኝ፣ የነገዋ ኢትዮጵያ በተስፋ እና በመተማመን የተመሠረተች ትሆናለች። ለዘመናት የቆዩ ቁርሾዎችን በጠረጴዛ ዙሪያ በመፍታት የሰላም ባህልን ማጠናከር የዚህ ሂደት ትልቁ ስኬት ነው።
በዚህ መድረክ ላይ የሚጻፉት ቃላት በወረቀት ላይ ብቻ አይቀሩም፤ ወደ ታሪክ በመሻገር ከአዳራሹ አልፈው የቀጣዮቹን ትውልዶች ሊመሩ የሚችሉ እና ተስፋን፣ ይቅርታን፣ የጋራ ራዕይን የሚተክሉ ናቸው።
በዚህም ሀገር የምትገነባው በዜጎቿ የተረጋጋ ውይይት በመሆኑ ወደ ምክክር መምጣት የድክመት ምልክት ሳይሆን የብስለት፣ የኃላፊነት እና የጋራ የወደፊት ዕጣ ፈንታን በሰላማዊ መንገድ ለመወሰን የተወሰደ ጠንካራ እርምጃ ነው።
መሣሪያን በብዕር የተኩ እጆች የሚጽፉት የአንድ ቡድን ታሪክ አይደለም፤ የሁሉም ኢትዮጵያውያን የጋራ የወደፊት ምዕራፍን ነው።
በልዩ እሸቱ
#nationaldialogue #peacebuilding #futureethiopia #inclusion #unityindiversity #reconciliation
Sponsored by
Surafel
4 days ago
«ከለውጡ በኋላ የነበረውን የመታፈን ስሜት ለማናፈስ በተደረገው ጥረት ውስጥ የተቀላቀሉ ቢምቢዎች ነበሩ»- ጠ/ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የ2010 ዓ.ም. የለውጥ ጉዞንና ከዚያ በኋላ በሀገሪቱ የፖለቲካ ምህዳር ውስጥ የታዩትን ኩነቶች አስመልክተው ከአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን ጋር ባደረጉት ቆይታ በሰጡት ማብራሪያ፣ የዐማራ ሕዝብ እንደማንኛውም የኢትዮጵያ ሕዝብ ለለውጥና ለዕድገት ከፍተኛ ተጋድሎ ማድረጉን ገልጸዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ እንደገለጹት፣ ከለውጡ ማግሥት የነበረው ጉዞ መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ በከፍተኛ ተስፋ የተሞላበት፣ «በዚህ ለውጥ እሠራለሁ፣ አተርፋለሁ፣ ሀገር አጠናለሁ» የሚል ሕልም በሰፊው የተገለጸበት ወቅት ነበር። ከለውጡ በፊት በነበረው የፖለቲካና የኢኮኖሚ ሥርዓት ውስጥ የመዘጋትና የመታፈን ምልክቶች እንደነበሩ የጠቆሙት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ የተዘጋን ቤት መስኮት ከፍቶ እንደማናፈስ ሁሉ ፖለቲካውንም ማናፈስ አስፈላጊ ነበር ብለዋል።
ሆኖም መስኮቶች ሲከፈቱ ንጹሕ አየር ብቻ ሳይሆን «ቢምቢዎችና ትንኞችም» አብረው እንደሚገቡ በመግለጽ፣ በፖለቲካው ምህዳር መከፈት ምክንያት አጋጣሚውን በመጠቀም ሁኔታዎችን ወደ ሥጋትና ድንግዝግዝነት ለመቀየር የሞከሩ አካላት እንደነበሩ አስረድተዋል።
«ቢምቢ በሳይዟ በጣም ትንሽ ናት፤ ነገር ግን ድምፅ በማሰማት እንዳትተኛ ታውክሃለች። ሁለተኛውና ከዚያ የሚከፋው ደግሞ በመንደፍ ደምን መምጠጧና በሽታ ማምጣቷ ነው። በኢትዮጵያ ፖለቲካ ዓውድ ውስጥም ከፍተኛ ድምፅ በማሰማት ለማወክ የሚሞክሩ፣ የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ለማደናቀፍና ህልውናዋን ለመገዳደር ከሚፈልጉ ኃይሎች ጋር እስከመሰለፍ የሄዱ አካላት ነበሩ።»
በወቅቱ በተፈጠሩት ነገሮች ምክንያት በሕዝቡ ዘንድ ምንድን ነው የመጣብን ሥጋት ተፈጥሮ የነበረ ቢሆንም፣ ነገሮች እያዋሉ እያደሩ ሲመጡ ግን የ«መደመር» መንገድ ብቸኛው አማራጭ መሆኑንና ለመበልጸግ የሚደረገው ጥረት ተገቢ መሆኑን ሕዝቡ ማመኑን ገልጸዋል።
በመጨረሻም፣ ሕዝቡ ይህንን እምነቱን በምርጫ ማረጋገጡን የጠቆሙት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ብቸኛው ኢትዮጵያን የማጽኛ መንገድ ታሪካዊውን ውህደትና እህትነት በሚያርቅ፣ በሚያድስና በሚያሰፋ መንገድ መሄድ፣ ተከባብሮና ተዋዶ በጋራ በመስራት ሀገርን ማጽናት ብቻ መሆኑን አብራርተዋል።
Seledadotio
Seledadotio
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የ2010 ዓ.ም. የለውጥ ጉዞንና ከዚያ በኋላ በሀገሪቱ የፖለቲካ ምህዳር ውስጥ የታዩትን ኩነቶች አስመልክተው ከአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን ጋር ባደረጉት ቆይታ በሰጡት ማብራሪያ፣ የዐማራ ሕዝብ እንደማንኛውም የኢትዮጵያ ሕዝብ ለለውጥና ለዕድገት ከፍተኛ ተጋድሎ ማድረጉን ገልጸዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ እንደገለጹት፣ ከለውጡ ማግሥት የነበረው ጉዞ መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ በከፍተኛ ተስፋ የተሞላበት፣ «በዚህ ለውጥ እሠራለሁ፣ አተርፋለሁ፣ ሀገር አጠናለሁ» የሚል ሕልም በሰፊው የተገለጸበት ወቅት ነበር። ከለውጡ በፊት በነበረው የፖለቲካና የኢኮኖሚ ሥርዓት ውስጥ የመዘጋትና የመታፈን ምልክቶች እንደነበሩ የጠቆሙት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ የተዘጋን ቤት መስኮት ከፍቶ እንደማናፈስ ሁሉ ፖለቲካውንም ማናፈስ አስፈላጊ ነበር ብለዋል።
ሆኖም መስኮቶች ሲከፈቱ ንጹሕ አየር ብቻ ሳይሆን «ቢምቢዎችና ትንኞችም» አብረው እንደሚገቡ በመግለጽ፣ በፖለቲካው ምህዳር መከፈት ምክንያት አጋጣሚውን በመጠቀም ሁኔታዎችን ወደ ሥጋትና ድንግዝግዝነት ለመቀየር የሞከሩ አካላት እንደነበሩ አስረድተዋል።
«ቢምቢ በሳይዟ በጣም ትንሽ ናት፤ ነገር ግን ድምፅ በማሰማት እንዳትተኛ ታውክሃለች። ሁለተኛውና ከዚያ የሚከፋው ደግሞ በመንደፍ ደምን መምጠጧና በሽታ ማምጣቷ ነው። በኢትዮጵያ ፖለቲካ ዓውድ ውስጥም ከፍተኛ ድምፅ በማሰማት ለማወክ የሚሞክሩ፣ የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ለማደናቀፍና ህልውናዋን ለመገዳደር ከሚፈልጉ ኃይሎች ጋር እስከመሰለፍ የሄዱ አካላት ነበሩ።»
በወቅቱ በተፈጠሩት ነገሮች ምክንያት በሕዝቡ ዘንድ ምንድን ነው የመጣብን ሥጋት ተፈጥሮ የነበረ ቢሆንም፣ ነገሮች እያዋሉ እያደሩ ሲመጡ ግን የ«መደመር» መንገድ ብቸኛው አማራጭ መሆኑንና ለመበልጸግ የሚደረገው ጥረት ተገቢ መሆኑን ሕዝቡ ማመኑን ገልጸዋል።
በመጨረሻም፣ ሕዝቡ ይህንን እምነቱን በምርጫ ማረጋገጡን የጠቆሙት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ብቸኛው ኢትዮጵያን የማጽኛ መንገድ ታሪካዊውን ውህደትና እህትነት በሚያርቅ፣ በሚያድስና በሚያሰፋ መንገድ መሄድ፣ ተከባብሮና ተዋዶ በጋራ በመስራት ሀገርን ማጽናት ብቻ መሆኑን አብራርተዋል።
Seledadotio
Seledadotio
5 days ago
በግብፅ ዳሚዬታ ወደብ በጋዝ መርከቦች ላይ የተፈጸመው የድሮን ጥቃት የኃይል ደኅንነትን አሳስቧል
#ethiopia | ግብፅ በሜዲትራኒያን ባሕር ዳርቻ በሚገኘው የዳሚዬታ (Damietta) ወደብ ላይ በቆሙ ሁለት የተፈጥሮ ጋዝ (LNG) መርከቦች ላይ በድሮን የተፈጸመ ጥቃት መከሰቱን በይፋ አረጋግጣለች።
ጥቃቱ በአንዱ መርከብ ላይ እሳት በማስነሳት ወደ ሌላው መርከብ ተዛምቶ ቢሆንም፣ በፍጥነት በተደረገ የአደጋ ምላሽ እሳቱ በቁጥጥር ስር ውሏል፤ በአደጋውም የሞተ ወይም የተጎዳ ሰው አልተመዘገበም።
በጥቃቱ የተጎዳው ዋና መርከብ በአሜሪካ ባለቤትነት የሚታወቀው Energos Winter የተሰኘ ተንቀሳቃሽ የጋዝ ማከማቻና ወደ ጋዝ የሚመልስ (FSRU) መርከብ ሲሆን፣ እሳቱ ወደ GasLog Salem የተባለ ሌላ የLNG መርከብ ተዛምቶ ነበር።
የባሕር ደኅንነት ተቋማት ጥቃቱ በድሮን መፈጸሙን ገልጸዋል።
ከጥቃቱ በኋላ የግብፅ ጠቅላይ ሚኒስትር ሙስጠፋ ማድቡሊ አገሪቱ የኤሌክትሪክና የተፈጥሮ ጋዝ ፍላጎቷን ለማሟላት አማራጭ የኃይል ምንጮችን አዘጋጅታለች ሲሉ አስታውቀዋል።
የፔትሮሊየም ሚኒስትሩም በግብፅ አራት የFSRU መርከቦች እና በዮርዳኖስ አቅጣጫ ወደብ ተጨማሪ አንድ መርከብ ዝግጁ መሆናቸውን ገልጸዋል።
በተጨማሪም የኤሌክትሪክ ሚኒስቴር በአገሪቱ የነዳጅ ክምችት በቂ መሆኑን እና የክረምት ወቅት ከፍተኛ የኃይል ፍላጎትን ለመሸፈን ዝግጅት መደረጉን ገልጿል።
እስካሁን ድረስ ማንም የጥቃቱን ኃላፊነት አልወሰደም። የግብፅ መንግሥት ምርመራ እያካሄደ እንደሆነ ገልጿል፤ ዓለም አቀፍ የዜና ተቋማትም የጥቃቱ አድራጊ ማን እንደሆነ እስካሁን በይፋ አልታወቀም ሲሉ ዘግበዋል።
ይህ ጥቃት የተፈጸመው በመካከለኛው ምሥራቅ የጦርነት ውጥረት በከፍተኛ ደረጃ በጨመረበት ወቅት ነው። የኃይል ገበያ ባለሙያዎች ጥቃቱ በሱዌዝ ካናልና በግብፅ የኃይል መሠረተ ልማቶች ደኅንነት ላይ ስጋት እንዲጨምር ማድረጉን ይገልጻሉ።
ነገር ግን እስካሁን ድረስ የሱዌዝ ካናል የመርከብ እንቅስቃሴ በቀጥታ እንዳልተስተጓጎለ ተነግሯል።
ዳሚዬታ የግብፅ ቁልፍ የLNG ማቀነባበሪያና የጋዝ ማስተላለፊያ ማዕከል ነው።
መንግሥቱ ከጥቂት ሳምንታት በፊት የዚህን ተቋም ዝግጁነት በመፈተሽ በምሥራቅ ሜዲትራኒያን የኃይል ማዕከል የመሆን ስትራቴጂዋን አረጋግጣ ነበር።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#ethiopia | ግብፅ በሜዲትራኒያን ባሕር ዳርቻ በሚገኘው የዳሚዬታ (Damietta) ወደብ ላይ በቆሙ ሁለት የተፈጥሮ ጋዝ (LNG) መርከቦች ላይ በድሮን የተፈጸመ ጥቃት መከሰቱን በይፋ አረጋግጣለች።
ጥቃቱ በአንዱ መርከብ ላይ እሳት በማስነሳት ወደ ሌላው መርከብ ተዛምቶ ቢሆንም፣ በፍጥነት በተደረገ የአደጋ ምላሽ እሳቱ በቁጥጥር ስር ውሏል፤ በአደጋውም የሞተ ወይም የተጎዳ ሰው አልተመዘገበም።
በጥቃቱ የተጎዳው ዋና መርከብ በአሜሪካ ባለቤትነት የሚታወቀው Energos Winter የተሰኘ ተንቀሳቃሽ የጋዝ ማከማቻና ወደ ጋዝ የሚመልስ (FSRU) መርከብ ሲሆን፣ እሳቱ ወደ GasLog Salem የተባለ ሌላ የLNG መርከብ ተዛምቶ ነበር።
የባሕር ደኅንነት ተቋማት ጥቃቱ በድሮን መፈጸሙን ገልጸዋል።
ከጥቃቱ በኋላ የግብፅ ጠቅላይ ሚኒስትር ሙስጠፋ ማድቡሊ አገሪቱ የኤሌክትሪክና የተፈጥሮ ጋዝ ፍላጎቷን ለማሟላት አማራጭ የኃይል ምንጮችን አዘጋጅታለች ሲሉ አስታውቀዋል።
የፔትሮሊየም ሚኒስትሩም በግብፅ አራት የFSRU መርከቦች እና በዮርዳኖስ አቅጣጫ ወደብ ተጨማሪ አንድ መርከብ ዝግጁ መሆናቸውን ገልጸዋል።
በተጨማሪም የኤሌክትሪክ ሚኒስቴር በአገሪቱ የነዳጅ ክምችት በቂ መሆኑን እና የክረምት ወቅት ከፍተኛ የኃይል ፍላጎትን ለመሸፈን ዝግጅት መደረጉን ገልጿል።
እስካሁን ድረስ ማንም የጥቃቱን ኃላፊነት አልወሰደም። የግብፅ መንግሥት ምርመራ እያካሄደ እንደሆነ ገልጿል፤ ዓለም አቀፍ የዜና ተቋማትም የጥቃቱ አድራጊ ማን እንደሆነ እስካሁን በይፋ አልታወቀም ሲሉ ዘግበዋል።
ይህ ጥቃት የተፈጸመው በመካከለኛው ምሥራቅ የጦርነት ውጥረት በከፍተኛ ደረጃ በጨመረበት ወቅት ነው። የኃይል ገበያ ባለሙያዎች ጥቃቱ በሱዌዝ ካናልና በግብፅ የኃይል መሠረተ ልማቶች ደኅንነት ላይ ስጋት እንዲጨምር ማድረጉን ይገልጻሉ።
ነገር ግን እስካሁን ድረስ የሱዌዝ ካናል የመርከብ እንቅስቃሴ በቀጥታ እንዳልተስተጓጎለ ተነግሯል።
ዳሚዬታ የግብፅ ቁልፍ የLNG ማቀነባበሪያና የጋዝ ማስተላለፊያ ማዕከል ነው።
መንግሥቱ ከጥቂት ሳምንታት በፊት የዚህን ተቋም ዝግጁነት በመፈተሽ በምሥራቅ ሜዲትራኒያን የኃይል ማዕከል የመሆን ስትራቴጂዋን አረጋግጣ ነበር።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
Comments