4 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የአሜሪካው ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ ከኢራን ጋር የሚደረገው ድርድር ዛሬ ሰኞ እንደሚቀጥል መናገራቸው ይታወቃል፡፡ ነገር ግን ኢራን ይህንን ዛሬ አስተባብላለች፡፡ እነዚህ ሁለት ተቃራኒ አቋሞች በሁለቱ አገራት መካከል የሚደረገውን ዲፕሎማሲያዊ ጥረት አስቸጋሪ አድርገውታል፡፡ እስካሁን ባለው ሁኔታ የሁለቱን አቋሞች በአጭሩ እንግለፅላችሁ፡፡
ፕሬዝደንት ትራምፕ ከኢራን ጋር የሚደረገው ድርድር ሰኞ እንደሚቀጥል ገልፀው ድርድሩ በሆርሙዝ ሰርጥ ጉዳይና የኢራንን ኒውክሌይር ጦር መሳሪያ የተመለከተ እንደሚሆን ተናግረዋል፡፡ በኢራን ላይ ሊያካሂዱት ያቀዱትን ‹‹ከባድ›› ጥቃት ያቆሙትም አጋሮቻቸው ዲፕሎማሲያዊ መፍትሄ እንዲመርጡ ስላሳሰቧቸው መሆኑን ገልፀዋል፡፡ ትላንት በሰጡት መግለጫ ‹‹በድርድር መልክ እየተነጋገርን ነው፡፡ ይህም ነገ ከሰአት ይጀምራል፡፡›› በማለት በእርግጠኝነት ተናግረው ነበር፡፡
አጋሮቻቸው ድርድሩ እንደሚደረግና ስምምነት ላይም እንደሚደረስ የነገሯቸው መሆኑን ጠቀሱት ትራምፕ ይህ ካልሆነ ግን ‹‹ከሁለተኛው የአለም ጦርነት ወዲህ ትልቁ›› የሚባለውን ጥቃት በኢራን ላይ እንደሚፈፅሙ አስታውቀዋል፡፡ የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቃል አቀባይ ኢስማኤል ባጋይ ግን በአሁኑ ጊዜ ከአሜሪካ ጋር የሚደረግ ምንም ድርድር የሌለ መሆኑን ከመግለፃቸውም በላይ በሚቀጥሉት ቀናት ውስጥም ተደራዳሪዎችን የመላክ እቅድ እንደሌላት አስረድተዋል፡፡ በአሁኑ ጊዜ ሆርሙዝ ሰርጥን በተመለከተ ድርድር እየተካሄደ ያለው ከኦማን ጋር መሆኑን ጠቅሰው ይህ ድርድር ጥሩ እየሄደ መሆኑንም ገልፀዋል፡፡ ይሁንና ከኦማን ጋር በሚደረግ ድርድር ብቻ ሆርሙዝ ሰርጥ እንደማይከፈት አስታውቀው አሜሪካ ጥቃት ከቀጠለች ሁኔታው ባለበት እንደሚቀጥል አስረድተዋል፡፡
ቃል አቀባዩ በዛሬ መግለጫቸው ከአሜሪካ ጋር ለማደራደር አዲስ አስታራቂ እንዳልመጣ ጠቅሰውም በሽምግልናው እየተሳተፉ ያሉት ፓኪስታንና ኳታር ብቻ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡ ቻይና እየጨመረ በመጣው ውጥረት ስጋት እንዳላት በመግለፅ ተጨማሪ ግጭት እንዳይመጣ እየሰራች እንደምትገኝም ጠቅሰዋል፡፡ አክለውም የየመንን ሁኔታ ከኢራን ጋር ማያያዝ ተገቢ አለመሆኑን ተናግረው ‹‹እንዲህ አይነት ጥረቶች ከሀላፊነት ለመሸሽ የሚደረጉ ናቸው›› ብለዋል፡፡
ፕሬዝደንት ትራምፕ ከኢራን ጋር የሚደረገው ድርድር ሰኞ እንደሚቀጥል ገልፀው ድርድሩ በሆርሙዝ ሰርጥ ጉዳይና የኢራንን ኒውክሌይር ጦር መሳሪያ የተመለከተ እንደሚሆን ተናግረዋል፡፡ በኢራን ላይ ሊያካሂዱት ያቀዱትን ‹‹ከባድ›› ጥቃት ያቆሙትም አጋሮቻቸው ዲፕሎማሲያዊ መፍትሄ እንዲመርጡ ስላሳሰቧቸው መሆኑን ገልፀዋል፡፡ ትላንት በሰጡት መግለጫ ‹‹በድርድር መልክ እየተነጋገርን ነው፡፡ ይህም ነገ ከሰአት ይጀምራል፡፡›› በማለት በእርግጠኝነት ተናግረው ነበር፡፡
አጋሮቻቸው ድርድሩ እንደሚደረግና ስምምነት ላይም እንደሚደረስ የነገሯቸው መሆኑን ጠቀሱት ትራምፕ ይህ ካልሆነ ግን ‹‹ከሁለተኛው የአለም ጦርነት ወዲህ ትልቁ›› የሚባለውን ጥቃት በኢራን ላይ እንደሚፈፅሙ አስታውቀዋል፡፡ የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቃል አቀባይ ኢስማኤል ባጋይ ግን በአሁኑ ጊዜ ከአሜሪካ ጋር የሚደረግ ምንም ድርድር የሌለ መሆኑን ከመግለፃቸውም በላይ በሚቀጥሉት ቀናት ውስጥም ተደራዳሪዎችን የመላክ እቅድ እንደሌላት አስረድተዋል፡፡ በአሁኑ ጊዜ ሆርሙዝ ሰርጥን በተመለከተ ድርድር እየተካሄደ ያለው ከኦማን ጋር መሆኑን ጠቅሰው ይህ ድርድር ጥሩ እየሄደ መሆኑንም ገልፀዋል፡፡ ይሁንና ከኦማን ጋር በሚደረግ ድርድር ብቻ ሆርሙዝ ሰርጥ እንደማይከፈት አስታውቀው አሜሪካ ጥቃት ከቀጠለች ሁኔታው ባለበት እንደሚቀጥል አስረድተዋል፡፡
ቃል አቀባዩ በዛሬ መግለጫቸው ከአሜሪካ ጋር ለማደራደር አዲስ አስታራቂ እንዳልመጣ ጠቅሰውም በሽምግልናው እየተሳተፉ ያሉት ፓኪስታንና ኳታር ብቻ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡ ቻይና እየጨመረ በመጣው ውጥረት ስጋት እንዳላት በመግለፅ ተጨማሪ ግጭት እንዳይመጣ እየሰራች እንደምትገኝም ጠቅሰዋል፡፡ አክለውም የየመንን ሁኔታ ከኢራን ጋር ማያያዝ ተገቢ አለመሆኑን ተናግረው ‹‹እንዲህ አይነት ጥረቶች ከሀላፊነት ለመሸሽ የሚደረጉ ናቸው›› ብለዋል፡፡
4 days ago
ኢራን ከአሜሪካ ጋር እየተነጋገርኩ አይደለም አለች
ኢራን ሰኞ ዕለት ከአሜሪካ ጋር ምንም ዓይነት ንግግር እያካሄደች አለመሆኗን ገልጻ፣ ከኦማን ጋር በሆርሙዝ ወሽመጥ ደኅንነቱ የተጠበቀ ጉዞ እንዲደረግ የሚያስችል “ጊዜያዊ የባህር መጓጓዣ መስመር” ለመመስረት እየሰራሁ ነው አለች።
የኢራን ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ እስማኤል ባጋይ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ ቴህራን ከሙስካት ጋር የምታደርገው ንግግር ቁልፍ በሆነው የባሕር መስመር ላይ ጊዜያዊ የመርከቦች መንቀሳቀሻ ለመመስረት ያለመ ነው ብለዋል።
ከኢራን መንግሥት ጋር ቅርበት ያለው ፋርስ የዜና ወኪል እንደዘገበው ባጋይ “ከኦማን ጋር የምናደርገው የአሁኑ ውይይት በሆርሙዝ ባህር ወሽመጥ ውስጥ የመርከቦችን ደኅንነቱ የተጠበቀ ጉዞ ማረጋገጥ ላይ ያተኮረ ነው” ብለዋል።
“በሆርሙዝ ባህር ወሽመጥ ውስጥ የመርከብ ጉዞ ደኅንነትን ለማረጋገጥ እንዲቻል፣ ከኦማን ጋር በመተባበር በተቻለ ፍጥነት ጊዜያዊ የመተላለፊያ መስመር ለመዘርጋት እየሰራን ነው” ሲሉም አክለዋል።
ባጋይ በቴህራን እና በዋሽንግተን መካከል ንግግር እየተደረገ ነው የሚሉ ዘገባዎችን ውድቅ በማድረግ “ከዩናይትድ ስቴትስ ጋር ድርድር እያደረግን አይደለም” ብለዋል።
የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከኢራን ጋር ሰኞ ከሰዓት በኋላ ውይይት እንደሚጀመር ትናንት እሁድ ተናግረው ነበር።
ትራምፕ፣ በሆርሙዝ ጉዳይ እና የኢራንን "ኒውክሌር ማስወገድ" በተመለከተ በቅርቡ ስምምነት ላይ መድረስ እንደሚቻል ያላቸውን ተስፋ ገልጸዋል ።
ባጋይ “አሜሪካ ጥቃቷን እና ክልከላዋን እስከቀጠለች ድረስ [በሆርሙዝ ያለው ሁኔታ ላይ] የሚለወጥ ነገር አይኖርም” ብለዋል።
BBC
ኢራን ሰኞ ዕለት ከአሜሪካ ጋር ምንም ዓይነት ንግግር እያካሄደች አለመሆኗን ገልጻ፣ ከኦማን ጋር በሆርሙዝ ወሽመጥ ደኅንነቱ የተጠበቀ ጉዞ እንዲደረግ የሚያስችል “ጊዜያዊ የባህር መጓጓዣ መስመር” ለመመስረት እየሰራሁ ነው አለች።
የኢራን ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ እስማኤል ባጋይ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ ቴህራን ከሙስካት ጋር የምታደርገው ንግግር ቁልፍ በሆነው የባሕር መስመር ላይ ጊዜያዊ የመርከቦች መንቀሳቀሻ ለመመስረት ያለመ ነው ብለዋል።
ከኢራን መንግሥት ጋር ቅርበት ያለው ፋርስ የዜና ወኪል እንደዘገበው ባጋይ “ከኦማን ጋር የምናደርገው የአሁኑ ውይይት በሆርሙዝ ባህር ወሽመጥ ውስጥ የመርከቦችን ደኅንነቱ የተጠበቀ ጉዞ ማረጋገጥ ላይ ያተኮረ ነው” ብለዋል።
“በሆርሙዝ ባህር ወሽመጥ ውስጥ የመርከብ ጉዞ ደኅንነትን ለማረጋገጥ እንዲቻል፣ ከኦማን ጋር በመተባበር በተቻለ ፍጥነት ጊዜያዊ የመተላለፊያ መስመር ለመዘርጋት እየሰራን ነው” ሲሉም አክለዋል።
ባጋይ በቴህራን እና በዋሽንግተን መካከል ንግግር እየተደረገ ነው የሚሉ ዘገባዎችን ውድቅ በማድረግ “ከዩናይትድ ስቴትስ ጋር ድርድር እያደረግን አይደለም” ብለዋል።
የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከኢራን ጋር ሰኞ ከሰዓት በኋላ ውይይት እንደሚጀመር ትናንት እሁድ ተናግረው ነበር።
ትራምፕ፣ በሆርሙዝ ጉዳይ እና የኢራንን "ኒውክሌር ማስወገድ" በተመለከተ በቅርቡ ስምምነት ላይ መድረስ እንደሚቻል ያላቸውን ተስፋ ገልጸዋል ።
ባጋይ “አሜሪካ ጥቃቷን እና ክልከላዋን እስከቀጠለች ድረስ [በሆርሙዝ ያለው ሁኔታ ላይ] የሚለወጥ ነገር አይኖርም” ብለዋል።
BBC
6 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ቅዳሜ ምሽት በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልእክት፣ የመካከለኛው ምስራቅ አጋሮች የአምስት ወሩን የኢራን ጦርነት ለማቆም የሚያስችል የስምምነት ማዕቀፍ ላይ መድረሳቸውን ገልጸው፣ ለጊዜው አዲስ ጥቃት ከመሰንዘር እንደሚታቀቡ አስታውቀዋል። ይህ አዲስ ስምምነት የሆርሙዝ የባህር ወሽመጥን በአፋጣኝ እና ሙሉ በሙሉ ክፍት ማድረግን እንዲሁም የኢራንን የኒውክሌር ስጋት ማብቃትን የሚያካትት መሆኑን ፕሬዝዳንቱ አክለዋል። ትራምፕ ለዓለም የወደፊት ጥቅም እንዲሁም ለኢራን ህልውና እና ብልጽግና ስል፣ በፍጥነት ስምምነት ላይ ለመድረስ በማሰብ ጥቃቱን ለመሰረዝ ተስማምቻለሁ ብለዋል። ጦርነቱን የሚያስቆመውን ይህንን ስምምነት ከዳር ለማድረስ በሚደረገው ጥረት፣ እስራኤል ከአሜሪካ ጋር ለመተባበር መስማማቷንም ጠቁመዋል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ፣የሳዑዲ አረቢያው አልጋ ወራሽ እና የሀገሪቱ መሪ ልዑል መሀመድ ቢን ሳልማን ቅዳሜ ዕለት ከትራምፕ ጋር በስልክ በተወያዩበት ወቅት፣ አሜሪካ ከኢራን ጋር ያላትን ግጭት ልታባብስ ትችላለች በሚል ስጋታቸውን ማቅረባቸውን ጉዳዩን በቅርበት የሚያውቁ ምንጮች ገልጸዋል። አክሲዮስ የተሰኘው የዜና አውታር እንደዘገበው፣ ይህ ውይይት የተካሄደው ትራምፕ በኢራን ላይ አዲስ ጥቃት ለመሰንዘር እያመነቱ ባለበት ወቅት ነው። ሳዑዲዎች፣ አሜሪካ የኢራንን የኃይል (ኢነርጂ) መሠረተ ልማቶች ላይ ጥቃት ከሰነዘረች፣ ቴህራን አጸፋውን በሳዑዲ እና በሌሎች የባህረ ሰላጤው ሀገራት የነዳጅ ተቋማት ላይ ልትወጣ ትችላለች የሚል ከፍተኛ ስጋት አድሮባቸዋል። አልጋ ወራሹ በዚህ የስልክ ውይይታቸው፣ ትራምፕ በኢራን ላይ ሊወስዱት ስላሰቡት አዲስ እርምጃ ማብራሪያ ጠይቀዋል። የዋይት ሀውስ ባለስልጣንም የሁለቱን መሪዎች የስልክ ውይይት መካሄድ አረጋግጠዋል።
ሳዑዲ አረቢያ በኢራን ከሚደገፉ የኢራቅ ሚሊሻዎች ጋር በተያያዘ ከአሜሪካ ጋር ወታደራዊ እርምጃዎችን ብትወስድም፣ ግጭቱ በድርድር እንዲፈታ ግፊት እያደረገች ትገኛለች። አልጋ ወራሹም የሳዑዲ መከላከያ ሚኒስትር የሆኑትን ወንድማቸውን ካሊድ ቢን ሳልማንን፣ ስለ ኢራን ስትራቴጂ ከትራምፕ እና ከምክትል ፕሬዝዳንት ጄዲ ቫንስ ጋር እንዲወያዩ ረቡዕ ዕለት ወደ ዋሽንግተን ልከው ነበር። በሌላ በኩል ትራምፕ ባለፈው ማክሰኞ ከእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንጃሚን ኔታንያሁ ጋር በዋይት ሀውስ የተወያዩ ሲሆን፣ የካቲት ወር ላይ ጦርነቱ ከጀመረ ወዲህ በአካል ሲገናኙ ይህ የመጀመሪያቸው ነው። የውይይቱ አካል የነበሩት የእስራኤሉ መሪ ትራምፕ በኢራን ላይ የሚያደርጉትን ጦርነት እንዲቀጥሉ አሳስበዋል።
ይህ የአሜሪካ ወታደራዊ እርምጃ ውጥረት ለትራምፕ እና ለፓርቲያቸው ከፍተኛ ፈተና ሆኗል። በብዙ አሜሪካውያን ዘንድ ተቀባይነት ያጣው ይህ ጦርነት፣ በመጪው ህዳር ወር ከሚካሄደው ወሳኝ የአጋማሽ ዘመን ምርጫ ጥቂት ወራት ቀደም ብሎ የዓለምን ኢኮኖሚ እያናጋው ይገኛል። ፕሬዝዳንቱ ከዚህ ቀደም ኢራን በዮርዳኖስ በሚገኘው የአሜሪካ የጦር ሰፈር ላይ ያደረሰችውን ድንገተኛ ጥቃት ተከትሎ አጸፋዊ እርምጃ እንደሚወስዱ ዝተው ነበር። አርብ ዕለትም አሜሪካ ኢራንን እጅግ አጥብቃ እንደምትመታ ተናግረው ነበር። የዋይት ሀውስ ፕሬዝዳንታዊ ቃል አቀባይ ካሮሊን ሊቪት በበኩላቸው፣ ቴህራን ባለፈው ወር ከአሜሪካ ጋር የተኩስ አቁም ስምምነት ተፈራርማ ወዲያውኑ ስምምነቱን በመጣስ በንግድ መርከቦች ላይ ተኩስ መክፈቷን እና አሜሪካውያን ወታደሮችን መግደሏን አስታውሰዋል።
ይህንኑ ከኢራን ጋር እየተባባሰ የመጣውን ውጥረት ተከትሎ፣ ቅዳሜ ዕለት የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በቀጠናው በሚገኙ 10 ሀገራት ለሚኖሩ አሜሪካውያን አዲስ የደህንነት ማስጠንቀቂያ አውጥቷል። ባሃሬን፣ እስራኤል፣ ኢራቅ፣ ዮርዳኖስ፣ ኩዌት፣ ሊባኖስ፣ ኦማን፣ ኳታር፣ ሳዑዲ አረቢያ እና የተባበሩት አረብ ኤምሬትስን በሚሸፍነው በዚህ ማስጠንቀቂያ፣ የአሜሪካ ዜጎች የበረራ ስረዛዎችን፣ ጊዜያዊ የአየር ክልል መዘጋትን እና ሌሎች የጉዞ መስተጓጎሎችን ታሳቢ በማድረግ ከፍተኛ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ አሳስቧል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ፣የሳዑዲ አረቢያው አልጋ ወራሽ እና የሀገሪቱ መሪ ልዑል መሀመድ ቢን ሳልማን ቅዳሜ ዕለት ከትራምፕ ጋር በስልክ በተወያዩበት ወቅት፣ አሜሪካ ከኢራን ጋር ያላትን ግጭት ልታባብስ ትችላለች በሚል ስጋታቸውን ማቅረባቸውን ጉዳዩን በቅርበት የሚያውቁ ምንጮች ገልጸዋል። አክሲዮስ የተሰኘው የዜና አውታር እንደዘገበው፣ ይህ ውይይት የተካሄደው ትራምፕ በኢራን ላይ አዲስ ጥቃት ለመሰንዘር እያመነቱ ባለበት ወቅት ነው። ሳዑዲዎች፣ አሜሪካ የኢራንን የኃይል (ኢነርጂ) መሠረተ ልማቶች ላይ ጥቃት ከሰነዘረች፣ ቴህራን አጸፋውን በሳዑዲ እና በሌሎች የባህረ ሰላጤው ሀገራት የነዳጅ ተቋማት ላይ ልትወጣ ትችላለች የሚል ከፍተኛ ስጋት አድሮባቸዋል። አልጋ ወራሹ በዚህ የስልክ ውይይታቸው፣ ትራምፕ በኢራን ላይ ሊወስዱት ስላሰቡት አዲስ እርምጃ ማብራሪያ ጠይቀዋል። የዋይት ሀውስ ባለስልጣንም የሁለቱን መሪዎች የስልክ ውይይት መካሄድ አረጋግጠዋል።
ሳዑዲ አረቢያ በኢራን ከሚደገፉ የኢራቅ ሚሊሻዎች ጋር በተያያዘ ከአሜሪካ ጋር ወታደራዊ እርምጃዎችን ብትወስድም፣ ግጭቱ በድርድር እንዲፈታ ግፊት እያደረገች ትገኛለች። አልጋ ወራሹም የሳዑዲ መከላከያ ሚኒስትር የሆኑትን ወንድማቸውን ካሊድ ቢን ሳልማንን፣ ስለ ኢራን ስትራቴጂ ከትራምፕ እና ከምክትል ፕሬዝዳንት ጄዲ ቫንስ ጋር እንዲወያዩ ረቡዕ ዕለት ወደ ዋሽንግተን ልከው ነበር። በሌላ በኩል ትራምፕ ባለፈው ማክሰኞ ከእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንጃሚን ኔታንያሁ ጋር በዋይት ሀውስ የተወያዩ ሲሆን፣ የካቲት ወር ላይ ጦርነቱ ከጀመረ ወዲህ በአካል ሲገናኙ ይህ የመጀመሪያቸው ነው። የውይይቱ አካል የነበሩት የእስራኤሉ መሪ ትራምፕ በኢራን ላይ የሚያደርጉትን ጦርነት እንዲቀጥሉ አሳስበዋል።
ይህ የአሜሪካ ወታደራዊ እርምጃ ውጥረት ለትራምፕ እና ለፓርቲያቸው ከፍተኛ ፈተና ሆኗል። በብዙ አሜሪካውያን ዘንድ ተቀባይነት ያጣው ይህ ጦርነት፣ በመጪው ህዳር ወር ከሚካሄደው ወሳኝ የአጋማሽ ዘመን ምርጫ ጥቂት ወራት ቀደም ብሎ የዓለምን ኢኮኖሚ እያናጋው ይገኛል። ፕሬዝዳንቱ ከዚህ ቀደም ኢራን በዮርዳኖስ በሚገኘው የአሜሪካ የጦር ሰፈር ላይ ያደረሰችውን ድንገተኛ ጥቃት ተከትሎ አጸፋዊ እርምጃ እንደሚወስዱ ዝተው ነበር። አርብ ዕለትም አሜሪካ ኢራንን እጅግ አጥብቃ እንደምትመታ ተናግረው ነበር። የዋይት ሀውስ ፕሬዝዳንታዊ ቃል አቀባይ ካሮሊን ሊቪት በበኩላቸው፣ ቴህራን ባለፈው ወር ከአሜሪካ ጋር የተኩስ አቁም ስምምነት ተፈራርማ ወዲያውኑ ስምምነቱን በመጣስ በንግድ መርከቦች ላይ ተኩስ መክፈቷን እና አሜሪካውያን ወታደሮችን መግደሏን አስታውሰዋል።
ይህንኑ ከኢራን ጋር እየተባባሰ የመጣውን ውጥረት ተከትሎ፣ ቅዳሜ ዕለት የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በቀጠናው በሚገኙ 10 ሀገራት ለሚኖሩ አሜሪካውያን አዲስ የደህንነት ማስጠንቀቂያ አውጥቷል። ባሃሬን፣ እስራኤል፣ ኢራቅ፣ ዮርዳኖስ፣ ኩዌት፣ ሊባኖስ፣ ኦማን፣ ኳታር፣ ሳዑዲ አረቢያ እና የተባበሩት አረብ ኤምሬትስን በሚሸፍነው በዚህ ማስጠንቀቂያ፣ የአሜሪካ ዜጎች የበረራ ስረዛዎችን፣ ጊዜያዊ የአየር ክልል መዘጋትን እና ሌሎች የጉዞ መስተጓጎሎችን ታሳቢ በማድረግ ከፍተኛ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ አሳስቧል።
6 days ago
ስደተኞቹ ሳይገቡ ወጥተዋል
#ethiopia | በትላንትናው እለት ከሞሮኮ መነሻቸውን አድርገው ስፔንን አጥለቅልቀው የነበሩት ስደተኞች ወደ መጡበት እየተመለሱ ይገኛል።
ኪዩታ ወደ ተሰኘችው የስፔን ከተማ የገቡት 60,000 የሚጠጉ ስደተኞቹ በዛሬው እለት ወደ ሞሮኮ በፍቃደኝነት እየተመለሱ መሆናቸውን አልጀዚራ ጽፏል።
የስፔን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጆዜ ማኑኤል አልቫሬዝ እንደገለፁት ሀገራቸው የስደተኞች ነፃነትና መብት እንደምታከብር ገልጸው ህገወጥ መንገድ ግን በየትኛውም መንገድ አንቀበልም ብለዋል።
አሁን በወጡ መረጃዎች መሠረት በህገወጥ መንገድ ከገቡት ስደተኞች መካከል 67 የሚሆኑት ህይወታቸው አልፏል ሲሉም ተናግረዋል።
የአውሮፓ ህብረት ሀላፊ ኡርሱላ ቮንደርላይን የስደተኞቹ ድርጊት ተቀባይነት እንደሌለው ተናግረው ሀገራት ድንበራቸውን ጥብቅ እንዲያደርጉ አሳስበዋል።
የፈረንሳይ የሀገር ውስጥ ሚኒስትር በበኩላቸው ሀገራቸውን ከስፔን የምትዋሰንበት ድንበር ማጠናከሯን ገልጸዋል።
የስፔኑ ጠቅላይ ሚኒስትር ፔድሮ ሳንቼዝ ድንበሮቻቸውን ክፍት አድርገው ስፔንን በስደተኞች እንድትወረር ያደረጉ ሀገራትን ክፍኛ ተችተዋል።
ሔኖክ ወ/ገብርኤል
#ethiopia #getutemesgen #getunews #spain #migrants #ceuta #europeanunion #ursulavonderleyen
#ethiopia | በትላንትናው እለት ከሞሮኮ መነሻቸውን አድርገው ስፔንን አጥለቅልቀው የነበሩት ስደተኞች ወደ መጡበት እየተመለሱ ይገኛል።
ኪዩታ ወደ ተሰኘችው የስፔን ከተማ የገቡት 60,000 የሚጠጉ ስደተኞቹ በዛሬው እለት ወደ ሞሮኮ በፍቃደኝነት እየተመለሱ መሆናቸውን አልጀዚራ ጽፏል።
የስፔን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጆዜ ማኑኤል አልቫሬዝ እንደገለፁት ሀገራቸው የስደተኞች ነፃነትና መብት እንደምታከብር ገልጸው ህገወጥ መንገድ ግን በየትኛውም መንገድ አንቀበልም ብለዋል።
አሁን በወጡ መረጃዎች መሠረት በህገወጥ መንገድ ከገቡት ስደተኞች መካከል 67 የሚሆኑት ህይወታቸው አልፏል ሲሉም ተናግረዋል።
የአውሮፓ ህብረት ሀላፊ ኡርሱላ ቮንደርላይን የስደተኞቹ ድርጊት ተቀባይነት እንደሌለው ተናግረው ሀገራት ድንበራቸውን ጥብቅ እንዲያደርጉ አሳስበዋል።
የፈረንሳይ የሀገር ውስጥ ሚኒስትር በበኩላቸው ሀገራቸውን ከስፔን የምትዋሰንበት ድንበር ማጠናከሯን ገልጸዋል።
የስፔኑ ጠቅላይ ሚኒስትር ፔድሮ ሳንቼዝ ድንበሮቻቸውን ክፍት አድርገው ስፔንን በስደተኞች እንድትወረር ያደረጉ ሀገራትን ክፍኛ ተችተዋል።
ሔኖክ ወ/ገብርኤል
#ethiopia #getutemesgen #getunews #spain #migrants #ceuta #europeanunion #ursulavonderleyen
9 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) ዘለንስኪ ‹‹300 ፓትሪዮት ሚሳኤል በአስቸኳይ እንዲሰጠን ጠይቄያለሁ›› አሉ፡፡ የዩክሬይኑ ፕሬዝደንት ዘለንስኪ ከአስክዮስ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ ፕሬዝደንት ትራምፕ 300 ፓትሪዮት ሚሳኤል እንዲሰጧቸው መጠየቃቸውን ገለፁ፡፡ ሲናገሩም ‹‹በዩክሬይን የሀይል መሰረተ ልማቶች ላይ የሚሰነዘሩ ጥቃቶችን ለማክሸፍ የፓትሪዮት አየር መከላከያ በአስቸኳይ እንዲቀርብልን ጠይቄያለሁ›› ብለዋል፡፡
ጨምረውም ‹‹የዩክሬይን የፓትሪዮት ሚሳኤል ክምችት እየተሟጠጠ ነው፡፡ ይህንን ካላገኘን ከባለስቲክ ሚሳኤል ራሳችንን መከላከል አንችልም፡፡ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በኬይቭ ላይ የሚደረገውን የሩሲያ ጥቃት መከላከል ያልቻልነው ለዚህ ነው›› ካሉ በኋላ ‹አስቸኳይ የክረምት ፓኬጅ›› እንደሚያስፈልጋቸው ገልፀዋል፡፡ አክለውም ‹‹ይህ ችግር በክረምቱ ካልተፈታ የሩሲያ የሚሳኤል ጥቃቶች የዩክሬይንን ሀይል ማመንጫዎች በማወደም ሚሊዮኖችን ካለማሞቂያ በማስቀረት ከፍተኛ ሰብአዊ ቀውስ ሊያስከትል ይችላል›› ያሉት ዘለንስኪ በመጪው የ3 ወራት ክረምት በእያንዳንዱ ወር 100 በጠቅላላው 300 ፓትሪዮት ሚሳኤል የግዴታ እንደሚያስፈልጋቸው አስረድተዋል፡፡
ምክንያቱም ሩሲያ በወር ውስጥ በአማካኝ ከ30 እስከ 40 ባለስቲክ ሚሳኤሎችን እንደምትጠቀም ገልፀዋል፡፡ ትራምፕ ለጥያቄያቸው መልስ ለመስጠት ጥረት እንደሚያደርጉ እንደገለፁላቸው ተናግረውም ይሁንና የተባለውን ለመፈፀም አስቸጋሪ መሆኑን እንዳስታወቁ አስረድተዋል፡፡ አሜሪካ ከኢራን ጋር እያደረገችው ባለው ጦርነት ለራሷ በርካታ ፓትሪዮት ሚሳኤል የምትፈልግ መሆኑ እንደተገለፀላቸው አስታውቀዋል፡፡ ዘለንስኪ እንዳሉት ሌላኛው አማራጭ የፓትሪዮት ሚሳኤልን የማምረት ፈቃድ ለዩክሬይን እንዲሰጣት ማድረግ ነው፡፡ ይሁንና ፈቃዱ ቢሰጣት እንኳ ለማምረት ከአንድ እስከ አምስት አመት የሚጠይቅ መሆኑ እንደተገለፀላቸው ያስታወቁት ዘለንስኪ ጨምረውም ‹‹ያም ሆነ ይህ ፓትሪዮት ያስፈልገናል›› በማለት በቃለ ምልልሱ አስታውቀዋል፡፡
ጨምረውም ‹‹የዩክሬይን የፓትሪዮት ሚሳኤል ክምችት እየተሟጠጠ ነው፡፡ ይህንን ካላገኘን ከባለስቲክ ሚሳኤል ራሳችንን መከላከል አንችልም፡፡ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በኬይቭ ላይ የሚደረገውን የሩሲያ ጥቃት መከላከል ያልቻልነው ለዚህ ነው›› ካሉ በኋላ ‹አስቸኳይ የክረምት ፓኬጅ›› እንደሚያስፈልጋቸው ገልፀዋል፡፡ አክለውም ‹‹ይህ ችግር በክረምቱ ካልተፈታ የሩሲያ የሚሳኤል ጥቃቶች የዩክሬይንን ሀይል ማመንጫዎች በማወደም ሚሊዮኖችን ካለማሞቂያ በማስቀረት ከፍተኛ ሰብአዊ ቀውስ ሊያስከትል ይችላል›› ያሉት ዘለንስኪ በመጪው የ3 ወራት ክረምት በእያንዳንዱ ወር 100 በጠቅላላው 300 ፓትሪዮት ሚሳኤል የግዴታ እንደሚያስፈልጋቸው አስረድተዋል፡፡
ምክንያቱም ሩሲያ በወር ውስጥ በአማካኝ ከ30 እስከ 40 ባለስቲክ ሚሳኤሎችን እንደምትጠቀም ገልፀዋል፡፡ ትራምፕ ለጥያቄያቸው መልስ ለመስጠት ጥረት እንደሚያደርጉ እንደገለፁላቸው ተናግረውም ይሁንና የተባለውን ለመፈፀም አስቸጋሪ መሆኑን እንዳስታወቁ አስረድተዋል፡፡ አሜሪካ ከኢራን ጋር እያደረገችው ባለው ጦርነት ለራሷ በርካታ ፓትሪዮት ሚሳኤል የምትፈልግ መሆኑ እንደተገለፀላቸው አስታውቀዋል፡፡ ዘለንስኪ እንዳሉት ሌላኛው አማራጭ የፓትሪዮት ሚሳኤልን የማምረት ፈቃድ ለዩክሬይን እንዲሰጣት ማድረግ ነው፡፡ ይሁንና ፈቃዱ ቢሰጣት እንኳ ለማምረት ከአንድ እስከ አምስት አመት የሚጠይቅ መሆኑ እንደተገለፀላቸው ያስታወቁት ዘለንስኪ ጨምረውም ‹‹ያም ሆነ ይህ ፓትሪዮት ያስፈልገናል›› በማለት በቃለ ምልልሱ አስታውቀዋል፡፡
Sponsored by
Surafel
18 days ago
ኢራን ከአሸማጋዮች የሰላም ዕቅድ እንደቀረበላት አስታወቀች
አሜሪካ እና ኢራንን በድጋሚ ወደ ተኩስ አቁም ስምምነት ለመመለስ ያቀዱት አሸማጋዮች፣ አዲስ የሰላም ዕቅድ ማቅረባቸውን ቴህራን አስታወቀች።
ሰኔ ላይ ጊዜያዊ የተኩስ አቁም ስምምነት ተፈራመው የነበሩት ሁለቱ አገራት፣ ላለፉት ሁለት ሳምንት ገደማ አንዳቸው በሌላቸው ላይ ከባድ ጥቃቶችን ሲፈጽሙ ቆይተዋል። የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕም ስምምነቱ አብቅቷል ብለዋል።
ይህንን ስምምነት ዳግም ለመመለስ ያቀዱት አሸማጋይ አገራት የ10 ቀናት የተኩስ አቁም እንዲደረግ የሚጠይቅ የሰላም ዕቅድ ማቅረባቸውን ዜና ወኪሉ ሮይተርስ ዘግቧል።
የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ኢስማኤል ባጋይ ዛሬ ሰኞ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ስለዚህ ጉዳይ ተጠይቀዋል። አሸማጋዮች ያዘጋጁትን ዕቅድ ለኢራን እንዳሳወቁ ቃል አቀባዩ አረጋግጠዋል።
“በአሸማጋዮች ስለዘተጋጁት ዕቅዶች ገለጻ ተደርጎል፤ ዕቅዱም ደርሶናል። ነገር ግን ለአሁኑ ወደ ዝርዝር ጉዳዮች ባንገባ ይሻላል” ሲሉ ተጨማሪ መረጃ ከመስጠት ተቆጥበዋል።
ባለፉት ቀናት ዲፕሎማሲያዊ እንቅስቃሴዎች እየተደረጉ መሆኑን የጠቆሙት ቃል አቀባዩ፤ “በአንዳንድ አሸማጋዮች የቀረቡ ዕቅዶች ለኢራን እስላማዊ ሪፐብሊክ መድረሳቸው የተረጋገጠ ነው” ብለዋል።
ፕሬዝዳንት ትራምፕ ወደፊት ለመደራደር የሚጠይቁ ከሆነ የኢራን ምላሽ ምን እንደሚሆንም ጥያቄ የቀረበላቸው ቃል አቀባዩ ኢስማኤል ባጋይ፣ “ዲፕሎማሲ ወይም ጦርነት” የሚል አማራጭ ለኢራን “ጠቃሚ አይደለም” ሲሉ ተናግረዋል።
“ራስን መከላከል ከዲፕሎማሲ ጋር አይጣጣምም ብሎ ማሰብ ትክክለኛ አመክንዮ አይደለም። [የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ] ሰይድ አባስ አራግቺ የሚያከናውኑት ሥራ እና [የመከላከያ ሚኒስትሩ] ሰይድ መጂድ የሚፈጽሙት ተግባር ተመሳሳይ ግብ የሚያሳኩ ናቸው” ብለዋል።
ባለፈው ሳምንት በመካከለኛው ምሥራቅ ጉብኝት ላይ የነበሩት የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ፤ ከጉዟቸው ሲመለሱ ከጋዜጠኞች ጋር በነበራቸው ቆይታ ዋሽንግተን “አሁንም ከኢራን ጋር ለሚደረግ ዲፕሎማሲያዊ መፍትሄ በሯ ክፍት” መሆኑን ተናግረው ነበር።
“ሁሌም ለዲፕሎማሲ ክፍት የሆንን ይመስለኛል። [መፍትሔው ግን] እውነተኛ መሆን አለበት። ልንገዛበት ፈቃደኛ የምንሆነው መሆን አለበት” ብለዋል።
ኢራን ሰኔ ላይ ለተፈረመው የመግባቢያ ስምምነት እንዳልተገዛች በመጥቀስ የከሰሱት ሩቢዮ፤ ሆርሙዝ ክፍት መሆን እንደነበረበት እንዲሁም በወሽመጡ የሚጓዙ መርከቦች ከጥቃት እና ከክፍያ ነጻ መሆን እንደነበረባቸው ገልጸዋል።
አሜሪካ ለዲፕሎማሲ ክፍት ስለመሆኗ የተነሳላቸው የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ኢስማኤል ባጋይ፣ “አሜሪካ ዲፕሎማሲ የምትለው ማስገደድ፣ ማስፈራራት፣ ዛቻ እና ማዕቀብ ነው” በማለት ተችተዋል።
BBC
አሜሪካ እና ኢራንን በድጋሚ ወደ ተኩስ አቁም ስምምነት ለመመለስ ያቀዱት አሸማጋዮች፣ አዲስ የሰላም ዕቅድ ማቅረባቸውን ቴህራን አስታወቀች።
ሰኔ ላይ ጊዜያዊ የተኩስ አቁም ስምምነት ተፈራመው የነበሩት ሁለቱ አገራት፣ ላለፉት ሁለት ሳምንት ገደማ አንዳቸው በሌላቸው ላይ ከባድ ጥቃቶችን ሲፈጽሙ ቆይተዋል። የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕም ስምምነቱ አብቅቷል ብለዋል።
ይህንን ስምምነት ዳግም ለመመለስ ያቀዱት አሸማጋይ አገራት የ10 ቀናት የተኩስ አቁም እንዲደረግ የሚጠይቅ የሰላም ዕቅድ ማቅረባቸውን ዜና ወኪሉ ሮይተርስ ዘግቧል።
የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ኢስማኤል ባጋይ ዛሬ ሰኞ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ስለዚህ ጉዳይ ተጠይቀዋል። አሸማጋዮች ያዘጋጁትን ዕቅድ ለኢራን እንዳሳወቁ ቃል አቀባዩ አረጋግጠዋል።
“በአሸማጋዮች ስለዘተጋጁት ዕቅዶች ገለጻ ተደርጎል፤ ዕቅዱም ደርሶናል። ነገር ግን ለአሁኑ ወደ ዝርዝር ጉዳዮች ባንገባ ይሻላል” ሲሉ ተጨማሪ መረጃ ከመስጠት ተቆጥበዋል።
ባለፉት ቀናት ዲፕሎማሲያዊ እንቅስቃሴዎች እየተደረጉ መሆኑን የጠቆሙት ቃል አቀባዩ፤ “በአንዳንድ አሸማጋዮች የቀረቡ ዕቅዶች ለኢራን እስላማዊ ሪፐብሊክ መድረሳቸው የተረጋገጠ ነው” ብለዋል።
ፕሬዝዳንት ትራምፕ ወደፊት ለመደራደር የሚጠይቁ ከሆነ የኢራን ምላሽ ምን እንደሚሆንም ጥያቄ የቀረበላቸው ቃል አቀባዩ ኢስማኤል ባጋይ፣ “ዲፕሎማሲ ወይም ጦርነት” የሚል አማራጭ ለኢራን “ጠቃሚ አይደለም” ሲሉ ተናግረዋል።
“ራስን መከላከል ከዲፕሎማሲ ጋር አይጣጣምም ብሎ ማሰብ ትክክለኛ አመክንዮ አይደለም። [የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ] ሰይድ አባስ አራግቺ የሚያከናውኑት ሥራ እና [የመከላከያ ሚኒስትሩ] ሰይድ መጂድ የሚፈጽሙት ተግባር ተመሳሳይ ግብ የሚያሳኩ ናቸው” ብለዋል።
ባለፈው ሳምንት በመካከለኛው ምሥራቅ ጉብኝት ላይ የነበሩት የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ፤ ከጉዟቸው ሲመለሱ ከጋዜጠኞች ጋር በነበራቸው ቆይታ ዋሽንግተን “አሁንም ከኢራን ጋር ለሚደረግ ዲፕሎማሲያዊ መፍትሄ በሯ ክፍት” መሆኑን ተናግረው ነበር።
“ሁሌም ለዲፕሎማሲ ክፍት የሆንን ይመስለኛል። [መፍትሔው ግን] እውነተኛ መሆን አለበት። ልንገዛበት ፈቃደኛ የምንሆነው መሆን አለበት” ብለዋል።
ኢራን ሰኔ ላይ ለተፈረመው የመግባቢያ ስምምነት እንዳልተገዛች በመጥቀስ የከሰሱት ሩቢዮ፤ ሆርሙዝ ክፍት መሆን እንደነበረበት እንዲሁም በወሽመጡ የሚጓዙ መርከቦች ከጥቃት እና ከክፍያ ነጻ መሆን እንደነበረባቸው ገልጸዋል።
አሜሪካ ለዲፕሎማሲ ክፍት ስለመሆኗ የተነሳላቸው የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ኢስማኤል ባጋይ፣ “አሜሪካ ዲፕሎማሲ የምትለው ማስገደድ፣ ማስፈራራት፣ ዛቻ እና ማዕቀብ ነው” በማለት ተችተዋል።
BBC
21 days ago
በትግራይ ሕዝብ ላይ የተጫነ የጥፋት ቡድን
የሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት በፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት ከተደመደመ በኋላ በስምምነቱ መሠረት በክልሉ ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን ከፌደራል መንግሥት እንዲሁም ከተቋቋመው ጊዜያዊ አስተዳደር በኩል ከፍተኛ ቁርጠኝነት ታይቶ ነበር።
በዚህም የትግራይ ሕዝብ የሰላም አየር እንዲተነፍስና ስለ መልሶ ግንባታና ልማት እንዲያስብ የሚያስችል ተስፋ ሰጪ ምዕራፍ ተከፍቶ እንደነበር ይታወሳል።
ነገር ግን ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጠነከረ የመጣው የሕገ ወጡ የህወሓት ቡድን የጥፋት አባዜ ለሰላምና ለመግባባት በቁርጠኝነት ሲሠሩ የነበሩትን የጊዜያዊ አስተዳደሩን መሪዎች ከአመራርነት በማንሸራተት በክልሉ ላይ አዲስ የውጥረት ነፋስ እንዲነፍስ እያደረገ ይገኛል።
የፌደራል መንግሥት ከ60 ሺህ በላይ ታጣቂዎችን ትጥቅ በማስፈታት፣ በማቋቋምና ወደ ማኅበረሰቡ በመመለስ የበኩሉን ታሪካዊ ኃላፊነት በስኬት ቢወጣም ህገ ወጡ ቡድን ግን አሁንም በሐሰት አሉባልታዎች ለክልሉ ህልውና ፈታኝ እንቅፋት እየሆነ ይገኛል።
የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር የቀድሞ ፕሬዚዳንት እና የጠቅላይ ሚኒስትሩ የምሥራቅ አፍሪካ ጉዳዮች አማካሪ ሚኒስትር አቶ ጌታቸው ረዳ በቅርቡ እንዳሉት፤ የትግራይ ሕዝብ የጥፋት መረብ በዘረጉ የስልጣን ጥመኛ ጥቂት ወንጀለኞች ታጋች ሆኗል።
ይህ ቡድን ሥልጣን ላይ በቆየበት ወቅት ሀገር ከማልማት ይልቅ የግል ጥቅምን ያስቀደመ ሲሆን፤ ዛሬም የክልሉን የልማት ተጠቃሚነት መና እያደረገው ይገኛል።
የትግራይ ሕዝብ አሁን ላይ “ያለፈው ይበቃናል” በማለት ለግጭት እምቢተኝነቱን በግልጽ እያሳየ ቢሆንም ሕገወጡ ቡድን ግን ዕድሜያቸው ያልደረሱ አዳጊ ወጣቶች ላይ ጭምር አፈሳና እገታ እየፈጸመ ሲሆን ይህ ተግባር የትግራይ ወጣት ቀዬውን ጥሎ እንዲሰደድ እያስገደደው ሲሆን ድርጊቱም በትግራይ እናቶች ዘንድ ከፍተኛ ተቃውሞና ቁጣን እያስነሳ ይገኛል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በቅርቡ በነበራቸው የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ውሎ የትግራይ ወጣቶች በጉልበት ታፍነው ለሱዳን ኃይሎች እስከመሸጥ መድረሳቸውንና ምንም ለማያውቁት ጦርነት ሕይወታቸውን እያጡ መሆኑን ገልጸዋል።
ከሁሉ በላይ አሳሳቢውና አደገኛው ጉዳይ፣ ይህ የጥፋት ቡድን የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም የማይሹ ታሪካዊ ጠላቶችን አጀንዳ አንግቦ፣ የሀገሪቱን የውስጥ ጥንካሬ ለማዳከም ሌት ተቀን ከሚሠራው የሻዕቢያ ሥርዓት ጋር ያደረገው ድብቅ ግንኙነት ነው።
በተለይም ኢትዮጵያ ዘላቂ ዕድገቷን ለማረጋገጥ ያነሳችውን የባሕር በር ጥያቄ ለማኮላሸት ከሚሠራው ሻዕቢያ ጋር የሚደረግ ይህ ግንኙነት ዳግም “የትሮይ ፈረስን” ወደ ክልሉ የማስገባት ያህል የከፋ አደጋ አለው።
ከፕሪቶሪያው ስምምነት በኋላ በትግራይ ሰላም መውረዱ እረፍት የነሳው ሻዕቢያ “ትግራይ ጨርሳ ካልጠፋች” በሚል እሳቤ ሲንቀሳቀስ የነበረ ሲሆን የሻዕቢያ ዋና ዓላማ በኢትዮጵያ ያሉ አኩራፊ ኃይሎችን በማደራጀት በሀገሪቱ የተረጋጋ ሰላም እንዳይኖር ማድረግ መሆኑን አቶ ጌታቸው ረዳ በሰጡት ትንታኔ አብራርተው ነበር።
ከዚህ በተጨማሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአንድ ወቅት በምክር ቤት በሰጡት ማብራሪያ፤ “የሻዕቢያ ሥርዓት ዳግም ሕዝባችንን እንዲበድል ዕድል አንሰጠውም፤ ከሞከረ የመጨረሻው ሙከራው ይሆናል” ሲሉ በጥብቅ አስጠንቅቀዋል።
ሻዕቢያ በኢትዮጵያ የውስጥ ኃይሎች ላይ መረብ በመዘርጋት ሉዓላዊነታችንን ለመፈታተን መሞከሩ ፍጹም ተቀባይነት የሌለው ተግባር ነው።
በሌላ በኩል ኢትዮጵያ የባሕር በር ማጣቷ ታሪካዊ፣ ሕጋዊና ኢኮኖሚያዊ ስህተት መሆኑን የጠቀሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ማንም ፈለገም አልፈለገም ትልቅ ሀገር የሆነችው ኢትዮጵያ ተዘግታ እንደማትኖርና በሰላማዊና በሰከነ ውይይት የባሕር በር የማግኘቷ ጉዳይ አይቀሬ መሆኑን በአጽንኦት ተናግረው ነበር።
አሁንም የፌደራል መንግሥት በትግራይ ክልል ምንም ዓይነት የጦርነት ዓላማ እንደሌለው ያረጋገጠ ሲሆን ይልቁንም ለሰላማዊ ውይይት እና ምክክር ጥሪ እያቀረበ ይገኛል።
ሀገራዊ ውይይትን የሽግግር ፍትሕንና ይቅርታን የመረጠው የመደመር መንግሥት ለሰላም ያለው በር ምንጊዜም ክፍት መሆኑን በተደጋጋሚ አረጋግጧል።
ሆኖም የሀገርን ሉዓላዊነት የሚፈታተን ማናቸውም ዓይነት የውጭ ትንኮሳና የውስጥ ተላላኪዎች የጥፋት እጅ ከመጣ መንግሥት ሀገሪቱን ለማስጠበቅ ከየትኛውም ጊዜ በላይ የተሟላ ዝግጁነት አለ።
የትግራይ ሕዝብ እውነተኛ መፍትሔ የሚያገኘው ከጥፋት አጋሮች ጋር በመሻረክ ሳይሆን የሰላምን አማራጭ በመቀበል ለልማትና ለትውልድ ግንባታ ሲሰለፍ ብቻ መሆኑ ሊታወቅ ይገባል።
በዮናስ ጌትነት
የሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት በፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት ከተደመደመ በኋላ በስምምነቱ መሠረት በክልሉ ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን ከፌደራል መንግሥት እንዲሁም ከተቋቋመው ጊዜያዊ አስተዳደር በኩል ከፍተኛ ቁርጠኝነት ታይቶ ነበር።
በዚህም የትግራይ ሕዝብ የሰላም አየር እንዲተነፍስና ስለ መልሶ ግንባታና ልማት እንዲያስብ የሚያስችል ተስፋ ሰጪ ምዕራፍ ተከፍቶ እንደነበር ይታወሳል።
ነገር ግን ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጠነከረ የመጣው የሕገ ወጡ የህወሓት ቡድን የጥፋት አባዜ ለሰላምና ለመግባባት በቁርጠኝነት ሲሠሩ የነበሩትን የጊዜያዊ አስተዳደሩን መሪዎች ከአመራርነት በማንሸራተት በክልሉ ላይ አዲስ የውጥረት ነፋስ እንዲነፍስ እያደረገ ይገኛል።
የፌደራል መንግሥት ከ60 ሺህ በላይ ታጣቂዎችን ትጥቅ በማስፈታት፣ በማቋቋምና ወደ ማኅበረሰቡ በመመለስ የበኩሉን ታሪካዊ ኃላፊነት በስኬት ቢወጣም ህገ ወጡ ቡድን ግን አሁንም በሐሰት አሉባልታዎች ለክልሉ ህልውና ፈታኝ እንቅፋት እየሆነ ይገኛል።
የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር የቀድሞ ፕሬዚዳንት እና የጠቅላይ ሚኒስትሩ የምሥራቅ አፍሪካ ጉዳዮች አማካሪ ሚኒስትር አቶ ጌታቸው ረዳ በቅርቡ እንዳሉት፤ የትግራይ ሕዝብ የጥፋት መረብ በዘረጉ የስልጣን ጥመኛ ጥቂት ወንጀለኞች ታጋች ሆኗል።
ይህ ቡድን ሥልጣን ላይ በቆየበት ወቅት ሀገር ከማልማት ይልቅ የግል ጥቅምን ያስቀደመ ሲሆን፤ ዛሬም የክልሉን የልማት ተጠቃሚነት መና እያደረገው ይገኛል።
የትግራይ ሕዝብ አሁን ላይ “ያለፈው ይበቃናል” በማለት ለግጭት እምቢተኝነቱን በግልጽ እያሳየ ቢሆንም ሕገወጡ ቡድን ግን ዕድሜያቸው ያልደረሱ አዳጊ ወጣቶች ላይ ጭምር አፈሳና እገታ እየፈጸመ ሲሆን ይህ ተግባር የትግራይ ወጣት ቀዬውን ጥሎ እንዲሰደድ እያስገደደው ሲሆን ድርጊቱም በትግራይ እናቶች ዘንድ ከፍተኛ ተቃውሞና ቁጣን እያስነሳ ይገኛል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በቅርቡ በነበራቸው የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ውሎ የትግራይ ወጣቶች በጉልበት ታፍነው ለሱዳን ኃይሎች እስከመሸጥ መድረሳቸውንና ምንም ለማያውቁት ጦርነት ሕይወታቸውን እያጡ መሆኑን ገልጸዋል።
ከሁሉ በላይ አሳሳቢውና አደገኛው ጉዳይ፣ ይህ የጥፋት ቡድን የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም የማይሹ ታሪካዊ ጠላቶችን አጀንዳ አንግቦ፣ የሀገሪቱን የውስጥ ጥንካሬ ለማዳከም ሌት ተቀን ከሚሠራው የሻዕቢያ ሥርዓት ጋር ያደረገው ድብቅ ግንኙነት ነው።
በተለይም ኢትዮጵያ ዘላቂ ዕድገቷን ለማረጋገጥ ያነሳችውን የባሕር በር ጥያቄ ለማኮላሸት ከሚሠራው ሻዕቢያ ጋር የሚደረግ ይህ ግንኙነት ዳግም “የትሮይ ፈረስን” ወደ ክልሉ የማስገባት ያህል የከፋ አደጋ አለው።
ከፕሪቶሪያው ስምምነት በኋላ በትግራይ ሰላም መውረዱ እረፍት የነሳው ሻዕቢያ “ትግራይ ጨርሳ ካልጠፋች” በሚል እሳቤ ሲንቀሳቀስ የነበረ ሲሆን የሻዕቢያ ዋና ዓላማ በኢትዮጵያ ያሉ አኩራፊ ኃይሎችን በማደራጀት በሀገሪቱ የተረጋጋ ሰላም እንዳይኖር ማድረግ መሆኑን አቶ ጌታቸው ረዳ በሰጡት ትንታኔ አብራርተው ነበር።
ከዚህ በተጨማሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአንድ ወቅት በምክር ቤት በሰጡት ማብራሪያ፤ “የሻዕቢያ ሥርዓት ዳግም ሕዝባችንን እንዲበድል ዕድል አንሰጠውም፤ ከሞከረ የመጨረሻው ሙከራው ይሆናል” ሲሉ በጥብቅ አስጠንቅቀዋል።
ሻዕቢያ በኢትዮጵያ የውስጥ ኃይሎች ላይ መረብ በመዘርጋት ሉዓላዊነታችንን ለመፈታተን መሞከሩ ፍጹም ተቀባይነት የሌለው ተግባር ነው።
በሌላ በኩል ኢትዮጵያ የባሕር በር ማጣቷ ታሪካዊ፣ ሕጋዊና ኢኮኖሚያዊ ስህተት መሆኑን የጠቀሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ማንም ፈለገም አልፈለገም ትልቅ ሀገር የሆነችው ኢትዮጵያ ተዘግታ እንደማትኖርና በሰላማዊና በሰከነ ውይይት የባሕር በር የማግኘቷ ጉዳይ አይቀሬ መሆኑን በአጽንኦት ተናግረው ነበር።
አሁንም የፌደራል መንግሥት በትግራይ ክልል ምንም ዓይነት የጦርነት ዓላማ እንደሌለው ያረጋገጠ ሲሆን ይልቁንም ለሰላማዊ ውይይት እና ምክክር ጥሪ እያቀረበ ይገኛል።
ሀገራዊ ውይይትን የሽግግር ፍትሕንና ይቅርታን የመረጠው የመደመር መንግሥት ለሰላም ያለው በር ምንጊዜም ክፍት መሆኑን በተደጋጋሚ አረጋግጧል።
ሆኖም የሀገርን ሉዓላዊነት የሚፈታተን ማናቸውም ዓይነት የውጭ ትንኮሳና የውስጥ ተላላኪዎች የጥፋት እጅ ከመጣ መንግሥት ሀገሪቱን ለማስጠበቅ ከየትኛውም ጊዜ በላይ የተሟላ ዝግጁነት አለ።
የትግራይ ሕዝብ እውነተኛ መፍትሔ የሚያገኘው ከጥፋት አጋሮች ጋር በመሻረክ ሳይሆን የሰላምን አማራጭ በመቀበል ለልማትና ለትውልድ ግንባታ ሲሰለፍ ብቻ መሆኑ ሊታወቅ ይገባል።
በዮናስ ጌትነት
24 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ፣ የባህረ ሰላጤው ሀገራት በሆርሙዝ ሰርጥ ለሚደረግላቸው ጥበቃ ምትክ በአሜሪካ ውስጥ በቢሊዮን የሚቆጠር ዶላር ኢንቨስት ለማድረግ ፍላጎት ማሳየታቸውን ይፋ አደረጉ። ፕሬዝዳንቱ ይህንን የተናገሩት በዋይት ሃውስ (ነጭ ቤተ መንግስት) ከኢራቅ ጠቅላይ ሚኒስትር ጋር በጋራ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ነው።
ትራምፕ ሰኞ ዕለት አሜሪካ በሆርሙዝ ሰርጥ በሚያልፉ መርከቦች ላይ የ20 በመቶ የታሪፍ ወይም የመተላለፊያ ክፍያ ልትጥል እንደምትችል ተናግረው የነበረ ቢሆንም፣ አሁን ላይ ግን "የክፍያ የሚለውን ሃሳብ አልወደድኩትም" ብለዋል። ይልቁንም በሰርጡ ለሚተላለፉ መርከቦች ማንም ሰው ክፍያ ሊያስከፍል እንደማይገባ ገልጸዋል።
እርሳቸው እንዳመለከቱት፣ ሰኞ ዕለት ካደረጉት ንግግር በኋላ የባህረ ሰላጤው ሀገራት ያነጋገሯቸው ሲሆን፣ ከክፍያ ይልቅ ሌላ የተሻለ አማራጭ ማቅረባቸውን ጠቅሰዋል። ሀገራቱ "ጉዳዩን በተለየ መንገድ ብናደርገው ደስ ይለናል፤ በአሜሪካ ውስጥ በቢሊዮን የሚቆጠሩ ዶላሮችን ኢንቨስት ማድረግ እንመርጣለን" ማለታቸውን ትራምፕ ይፋ አድርገዋል።
ፕሬዝዳንት ትራምፕ ንግግራቸውን ሲያጠቃልሉም አሜሪካ ለሆርሙዝ ሰርጥ ጥበቃ የምታደርግበትን ሁኔታ በመደገፍ፣ የባህረ ሰላጤው ሀገራት በሀገሪቱ ውስጥ የሚያደርጉትን ግዙፍ ኢንቨስትመንት በደስታ እንደምትቀበል በይፋ አረጋግጠዋል።
ትራምፕ ሰኞ ዕለት አሜሪካ በሆርሙዝ ሰርጥ በሚያልፉ መርከቦች ላይ የ20 በመቶ የታሪፍ ወይም የመተላለፊያ ክፍያ ልትጥል እንደምትችል ተናግረው የነበረ ቢሆንም፣ አሁን ላይ ግን "የክፍያ የሚለውን ሃሳብ አልወደድኩትም" ብለዋል። ይልቁንም በሰርጡ ለሚተላለፉ መርከቦች ማንም ሰው ክፍያ ሊያስከፍል እንደማይገባ ገልጸዋል።
እርሳቸው እንዳመለከቱት፣ ሰኞ ዕለት ካደረጉት ንግግር በኋላ የባህረ ሰላጤው ሀገራት ያነጋገሯቸው ሲሆን፣ ከክፍያ ይልቅ ሌላ የተሻለ አማራጭ ማቅረባቸውን ጠቅሰዋል። ሀገራቱ "ጉዳዩን በተለየ መንገድ ብናደርገው ደስ ይለናል፤ በአሜሪካ ውስጥ በቢሊዮን የሚቆጠሩ ዶላሮችን ኢንቨስት ማድረግ እንመርጣለን" ማለታቸውን ትራምፕ ይፋ አድርገዋል።
ፕሬዝዳንት ትራምፕ ንግግራቸውን ሲያጠቃልሉም አሜሪካ ለሆርሙዝ ሰርጥ ጥበቃ የምታደርግበትን ሁኔታ በመደገፍ፣ የባህረ ሰላጤው ሀገራት በሀገሪቱ ውስጥ የሚያደርጉትን ግዙፍ ኢንቨስትመንት በደስታ እንደምትቀበል በይፋ አረጋግጠዋል።
1 month ago
እንኳን ደስ አላችሁ - ከለቡ ገብርኤል የምሥራች ተሠማ
ከ100,000,000.00 - ከአንድ መቶ ሚሊዮን ብር በላይ በመሰብሰብ በድል ተጠናቀቀ
የለቡ ምሥራቀ ፀሐይ ቅዱስ ገብርኤል ሕንጻ ቤተክርስቲያኑን ለማጠናቀቅ ሰኔ 27 እና 28 በተከናወነው የገቢ ማሰባሰቢያ የእራት ግብዣ እና የገቢ ማሰባሰቢያ ከ100 ሚሊዮን ብር በላይ በጥሬ ገንዘብ እና በቃል ኪዳን ሰነድ ተሰብስቧል ።
ከ13 ዓመታት በፊት የመሠረት ድንጋይ ተቀምጦ ወደ ግንባታ የገባው በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ቤተ ክህነት ሥር የሚገኘው የለቡ ምሥራቀ ፀሐይ ቅዱስ ገብርኤል እና መርጡለ ቅድስት አርሴማ ወአቡነ አዳም ገዳም በውስጡ የቅድስት አርሴማ ቤተክርስቲያን እና ምሥራቀ ፀሐይ ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያንን የያዘ ነው።
በደብሩ የሚገኘው የቅድስት አርሴማ ሕንጻ ቤተመቅደስ በአቶ ሰማቸው ከበደን እና ቤተሰቦቻቸው ሙሉ ወጪ ተገንብቶ ቤተክርስቲያኑ ለአገልግሎት መብቃቱን የደብሩ አስተዳዳሪ መልአከ ጽዮን ቆሞስ አባ አስጠፋኖስ ይርጋ አስተታውሰዋል።
አስተዳዳሪው እዚያው ግቢ ውስጥ ከቅድስት አርሴማ ቤተክርስቲያን ቀድሞ የመሠረት ድንጋይ ተጥሎ ከቅድስት አርሴማ በኋላም እንኳ ማለቅ ያልቻለው የለቡ ምሥራቀ ፀሐይ ቅዱስ ገብርኤል ሕንጻ ቤተክርስቲያንን ለማጠናቀቅ ሰኔ 27 እና 28 በኢንተር ሌግዠሪ ሆቴል የተከናወነው የገቢ ማሰባሰቢያ የእራት ግብዣ እና የገቢ ማሰባሰቢያ ሕንጻውን ለማጠናቀቅ ከ100 ሚሊዮን ብር በላይ በጥሬ ገንዘብ እና በቃል ኪዳን ሰነድ ተሰብስቦ በስኬት መጠናቀቁን አስታውቀዋል።
የደብሩ ሰበካ ጉባኤ ምክትል ሊቀ መንበር መጋቤ አእላፍ ጸጋዬ ቸሩ በግላቸው 9 ሚሊዮን ብር ድጋፍ ማድረጋቸውን የገለጹት አስተዳዳሪው ፣ በደብሩ አስተዳዳሪ አስተባባሪነት ወልደጊዮርጊስ ተብሎ በጥምቀት ስሙ የተገለጸ የቅድስት ቤተክርስቲያን ልጅ 10 ሚሊዮን ብር በላይ በማውጣት ለመርጡለ ቅድስት አርሴማ ቤተክርስቲያን የክርስትና ቤት ለመሥራት ቃል መግባቱን ገልጸዋል።
የደብሩ አስተዳዳሪ መልአከ ጽዮን ቆሞስ አባ አስጢፋኖስ በዚህ የገቢ ማሰባሰቢያ አቶ ሰማቸው ከበደን እና ባለቤታቸውን ወ/ሮ ሀናን ጨምሮ የተለያዩ ተቋማትና በመላው ዓለም የሚገኙ ምእመናን ላደረጉት ተሳትፎ ምስጋናቸውን አቅርበዋል ።
በተለይም አቶ ስማቸው ከበደ በሆቴላቸው መርሐ ግብሩ በነጻ እንዲከናወን ከአምስት ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት ነጻ አገልግሎት መስጠታቸው እና የገንዘብ ድጋፍ ማድረጋቸውን ገልጸው ለሌሎች ባለሀብቶችም አርአያነታቸው የጎላ መሆኑን ገልጸዋል።
ደብሩ ገቢ የተደረገውን እና በቃል ኪዳን ሰነድ ቃል የተገባውን ገንዘብ በመሰብሰብ በአጭር ጊዜ ቀሪውን የማጠናቀቂያ ሥራ ፈጽሞ ሕንጻ ቤተመቅደሱን ወደ አገልግሎት ለማስገባት የሕንጻ አሠሪ ኮሚቴው በሥራ ላይ መሆኑን ገልጸዋል ።
የለቡ ምሥራቀ ፀሐይ ቅዱስ ገብርኤል እና መርጡለ ቅድስት አርሴማ ወአቡነ አዳም ገዳም በ1986 ዓ.ም የተመሠረተ ደብር ነው።
ኹነቱን በበጎ አድራጎት ያስተባበረው ሎዛ ኹነቶች አዘጋጅ መኾኑን የገዳሙ አስተዳዳሪ መልአከ ጽዮን ቆሞስ አባ እስጢፋኖስ ይርጋ ተናግረው ለሚዲያዎች፣ ለአገልጋዮች እና ለምእመናን ምስጋናቸውን አቅርበዋል
ከ100,000,000.00 - ከአንድ መቶ ሚሊዮን ብር በላይ በመሰብሰብ በድል ተጠናቀቀ
የለቡ ምሥራቀ ፀሐይ ቅዱስ ገብርኤል ሕንጻ ቤተክርስቲያኑን ለማጠናቀቅ ሰኔ 27 እና 28 በተከናወነው የገቢ ማሰባሰቢያ የእራት ግብዣ እና የገቢ ማሰባሰቢያ ከ100 ሚሊዮን ብር በላይ በጥሬ ገንዘብ እና በቃል ኪዳን ሰነድ ተሰብስቧል ።
ከ13 ዓመታት በፊት የመሠረት ድንጋይ ተቀምጦ ወደ ግንባታ የገባው በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ቤተ ክህነት ሥር የሚገኘው የለቡ ምሥራቀ ፀሐይ ቅዱስ ገብርኤል እና መርጡለ ቅድስት አርሴማ ወአቡነ አዳም ገዳም በውስጡ የቅድስት አርሴማ ቤተክርስቲያን እና ምሥራቀ ፀሐይ ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያንን የያዘ ነው።
በደብሩ የሚገኘው የቅድስት አርሴማ ሕንጻ ቤተመቅደስ በአቶ ሰማቸው ከበደን እና ቤተሰቦቻቸው ሙሉ ወጪ ተገንብቶ ቤተክርስቲያኑ ለአገልግሎት መብቃቱን የደብሩ አስተዳዳሪ መልአከ ጽዮን ቆሞስ አባ አስጠፋኖስ ይርጋ አስተታውሰዋል።
አስተዳዳሪው እዚያው ግቢ ውስጥ ከቅድስት አርሴማ ቤተክርስቲያን ቀድሞ የመሠረት ድንጋይ ተጥሎ ከቅድስት አርሴማ በኋላም እንኳ ማለቅ ያልቻለው የለቡ ምሥራቀ ፀሐይ ቅዱስ ገብርኤል ሕንጻ ቤተክርስቲያንን ለማጠናቀቅ ሰኔ 27 እና 28 በኢንተር ሌግዠሪ ሆቴል የተከናወነው የገቢ ማሰባሰቢያ የእራት ግብዣ እና የገቢ ማሰባሰቢያ ሕንጻውን ለማጠናቀቅ ከ100 ሚሊዮን ብር በላይ በጥሬ ገንዘብ እና በቃል ኪዳን ሰነድ ተሰብስቦ በስኬት መጠናቀቁን አስታውቀዋል።
የደብሩ ሰበካ ጉባኤ ምክትል ሊቀ መንበር መጋቤ አእላፍ ጸጋዬ ቸሩ በግላቸው 9 ሚሊዮን ብር ድጋፍ ማድረጋቸውን የገለጹት አስተዳዳሪው ፣ በደብሩ አስተዳዳሪ አስተባባሪነት ወልደጊዮርጊስ ተብሎ በጥምቀት ስሙ የተገለጸ የቅድስት ቤተክርስቲያን ልጅ 10 ሚሊዮን ብር በላይ በማውጣት ለመርጡለ ቅድስት አርሴማ ቤተክርስቲያን የክርስትና ቤት ለመሥራት ቃል መግባቱን ገልጸዋል።
የደብሩ አስተዳዳሪ መልአከ ጽዮን ቆሞስ አባ አስጢፋኖስ በዚህ የገቢ ማሰባሰቢያ አቶ ሰማቸው ከበደን እና ባለቤታቸውን ወ/ሮ ሀናን ጨምሮ የተለያዩ ተቋማትና በመላው ዓለም የሚገኙ ምእመናን ላደረጉት ተሳትፎ ምስጋናቸውን አቅርበዋል ።
በተለይም አቶ ስማቸው ከበደ በሆቴላቸው መርሐ ግብሩ በነጻ እንዲከናወን ከአምስት ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት ነጻ አገልግሎት መስጠታቸው እና የገንዘብ ድጋፍ ማድረጋቸውን ገልጸው ለሌሎች ባለሀብቶችም አርአያነታቸው የጎላ መሆኑን ገልጸዋል።
ደብሩ ገቢ የተደረገውን እና በቃል ኪዳን ሰነድ ቃል የተገባውን ገንዘብ በመሰብሰብ በአጭር ጊዜ ቀሪውን የማጠናቀቂያ ሥራ ፈጽሞ ሕንጻ ቤተመቅደሱን ወደ አገልግሎት ለማስገባት የሕንጻ አሠሪ ኮሚቴው በሥራ ላይ መሆኑን ገልጸዋል ።
የለቡ ምሥራቀ ፀሐይ ቅዱስ ገብርኤል እና መርጡለ ቅድስት አርሴማ ወአቡነ አዳም ገዳም በ1986 ዓ.ም የተመሠረተ ደብር ነው።
ኹነቱን በበጎ አድራጎት ያስተባበረው ሎዛ ኹነቶች አዘጋጅ መኾኑን የገዳሙ አስተዳዳሪ መልአከ ጽዮን ቆሞስ አባ እስጢፋኖስ ይርጋ ተናግረው ለሚዲያዎች፣ ለአገልጋዮች እና ለምእመናን ምስጋናቸውን አቅርበዋል
1 month ago
እንኳን ደስ አላችሁ - ከለቡ ገብርኤል የምሥራችጨተሠማ
ከ100,000,000.00 - ከአንድ መቶ ሚሊያን ብር በላይ በመሰብሰብ በድል ተጠናቀቀ
የለቡ ምሥራቀ ፀሐይ ቅዱስ ገብርኤል ሕንጻ ቤተክርስቲያኑን ለማጠናቀቅ ሰኔ 27 እና 28 በተከናወነው የገቢ ማሰባሰቢያ የእራት ግብዣ እና የገቢ ማሰባሰቢያ ከ100 ሚሊዮን ብር በላይ በጥሬ ገንዘብ እና በቃል ኪዳን ሰነድ ተሰብስቧል ።
ከ13 ዓመታት በፊት የመሠረት ድንጋይ ተቀምጦ ወደ ግንባታ የገባው በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ቤተ ክህነት ሥር የሚገኘው የለቡ ምሥራቀ ፀሐይ ቅዱስ ገብርኤል እና መርጡለ ቅድስት አርሴማ ወአቡነ አዳም ገዳም
በውስጡ የቅድስት አርሴማ ቤተክርስቲያን እና ምሥራቀ ፀሐይ ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያንን የያዘ ነው።
በደብሩ የሚገኘው የቅድስት አርሴማ ሕንጻ ቤተመቅደስ በአቶ ሰማቸው ከበደን እና ቤተሰቦቻቸው ሙሉ ወጪ ተገንብቶ ቤተክርስቲያኑ ለአገልግሎት መብቃቱን የደብሩ አስተዳዳሪ መልአከ ጽዮን ቆሞስ አባ አስጠፋኖስ ይርጋ አስተታውሰዋል።
አስተዳዳሪው እዚያው ግቢ ውስጥ ከቅድስት አርሴማ ቤተክርስቲያን ቀድሞ የመሠረት ድንጋይ ተጥሎ ከቅድስት አርሴማ በኋላም እንኳ ማለቅ ያልቻለው የለቡ ምሥራቀ ፀሐይ ቅዱስ ገብርኤል ሕንጻ ቤተክርስቲያንን ለማጠናቀቅ ሰኔ 27 እና 28 በኢንተር ሌግዠሪ ሆቴል የተከናወነው የገቢ ማሰባሰቢያ የእራት ግብዣ እና የገቢ ማሰባሰቢያ ሕንጻውን ለማጠናቀቅ ከ100 ሚሊዮን ብር በላይ በጥሬ ገንዘብ እና በቃል ኪዳን ሰነድ ተሰብስቦ በስኬት መጠናቀቁን አስታውቀዋል።
የደብሩ ሰበካ ጉባኤ ምክትል ሊቀ መንበር መጋቤ አእላፍ ጸጋዬ ቸሩ በግላቸው 9 ሚሊዮን ብር ድጋፍ ማድረጋቸውን የገለጹት አስተዳዳሪው ፣ በደብሩ አስተዳዳሪ አስተባባሪነት ወልደጊዮርጊስ ተብሎ በጥምቀት ስሙ የተገለጸ የቅድስት ቤተክርስቲያን ልጅ 10 ሚሊዮን ብር በላይ በማውጣት ለመርጡለ ቅድስት አርሴማ ቤተክርስቲያን የክርስትና ቤት ለመሥራት ቃል መግባቱን ገልጸዋል።
የደብሩ አስተዳዳሪ መልአከ ጽዮን ቆሞስ አባ አስጢፋኖስ በዚህ የገቢ ማሰባሰቢያ አቶ ሰማቸው ከበደን እና ባለቤታቸውን ወ/ሮ ሀናን ጨምሮ የተለያዩ ተቋማትና በመላው ዓለም የሚገኙ ምእመናን ላደረጉት ተሳትፎ ምስጋናቸውን አቅርበዋል ።
በተለይም አቶ ስማቸው ከበደ በሆቴላቸው መርሐ ግብሩ በነጻ እንዲከናወን ከአምስት ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት ነጻ አገልግሎት መስጠታቸው እና የገንዘብ ድጋፍ ማድረጋቸውን ገልጸው ለሌሎች ባለሀብቶችም አርአያነታቸው የጎላ መሆኑን ገልጸዋል።
ደብሩ ገቢ የተደረገውን እና በቃል ኪዳን ሰነድ ቃል የተገባውን ገንዘብ በመሰብሰብ በአጭር ጊዜ ቀሪውን የማጠናቀቂያ ሥራ ፈጽሞ ሕንጻ ቤተመቅደሱን ወደ አገልግሎት ለማስገባት የሕንጻ አሠሪ ኮሚቴው በሥራ ላይ መሆኑን ገልጸዋል ።
የለቡ ምሥራቀ ፀሐይ ቅዱስ ገብርኤል እና መርጡለ ቅድስት አርሴማ ወአቡነ አዳም ገዳም በ1986 ዓ.ም የተመሠረተ ደብር ነው።
ኹነቱን በበጎ አድራጎት ያስተባበረው ሎዛ ኹነቶች አዘጋጅ መኾኑን የገዳሙ አስተዳዳሪ መልአከ ጽዮን ቆሞስ አባ እስጢፋኖስ ይርጋ ተናግረው ለሚዲያዎች፣ ለአገልጋዮች እና ለምእመናን ምስጋናቸውን አቅርበዋል
ከ100,000,000.00 - ከአንድ መቶ ሚሊያን ብር በላይ በመሰብሰብ በድል ተጠናቀቀ
የለቡ ምሥራቀ ፀሐይ ቅዱስ ገብርኤል ሕንጻ ቤተክርስቲያኑን ለማጠናቀቅ ሰኔ 27 እና 28 በተከናወነው የገቢ ማሰባሰቢያ የእራት ግብዣ እና የገቢ ማሰባሰቢያ ከ100 ሚሊዮን ብር በላይ በጥሬ ገንዘብ እና በቃል ኪዳን ሰነድ ተሰብስቧል ።
ከ13 ዓመታት በፊት የመሠረት ድንጋይ ተቀምጦ ወደ ግንባታ የገባው በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ቤተ ክህነት ሥር የሚገኘው የለቡ ምሥራቀ ፀሐይ ቅዱስ ገብርኤል እና መርጡለ ቅድስት አርሴማ ወአቡነ አዳም ገዳም
በውስጡ የቅድስት አርሴማ ቤተክርስቲያን እና ምሥራቀ ፀሐይ ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያንን የያዘ ነው።
በደብሩ የሚገኘው የቅድስት አርሴማ ሕንጻ ቤተመቅደስ በአቶ ሰማቸው ከበደን እና ቤተሰቦቻቸው ሙሉ ወጪ ተገንብቶ ቤተክርስቲያኑ ለአገልግሎት መብቃቱን የደብሩ አስተዳዳሪ መልአከ ጽዮን ቆሞስ አባ አስጠፋኖስ ይርጋ አስተታውሰዋል።
አስተዳዳሪው እዚያው ግቢ ውስጥ ከቅድስት አርሴማ ቤተክርስቲያን ቀድሞ የመሠረት ድንጋይ ተጥሎ ከቅድስት አርሴማ በኋላም እንኳ ማለቅ ያልቻለው የለቡ ምሥራቀ ፀሐይ ቅዱስ ገብርኤል ሕንጻ ቤተክርስቲያንን ለማጠናቀቅ ሰኔ 27 እና 28 በኢንተር ሌግዠሪ ሆቴል የተከናወነው የገቢ ማሰባሰቢያ የእራት ግብዣ እና የገቢ ማሰባሰቢያ ሕንጻውን ለማጠናቀቅ ከ100 ሚሊዮን ብር በላይ በጥሬ ገንዘብ እና በቃል ኪዳን ሰነድ ተሰብስቦ በስኬት መጠናቀቁን አስታውቀዋል።
የደብሩ ሰበካ ጉባኤ ምክትል ሊቀ መንበር መጋቤ አእላፍ ጸጋዬ ቸሩ በግላቸው 9 ሚሊዮን ብር ድጋፍ ማድረጋቸውን የገለጹት አስተዳዳሪው ፣ በደብሩ አስተዳዳሪ አስተባባሪነት ወልደጊዮርጊስ ተብሎ በጥምቀት ስሙ የተገለጸ የቅድስት ቤተክርስቲያን ልጅ 10 ሚሊዮን ብር በላይ በማውጣት ለመርጡለ ቅድስት አርሴማ ቤተክርስቲያን የክርስትና ቤት ለመሥራት ቃል መግባቱን ገልጸዋል።
የደብሩ አስተዳዳሪ መልአከ ጽዮን ቆሞስ አባ አስጢፋኖስ በዚህ የገቢ ማሰባሰቢያ አቶ ሰማቸው ከበደን እና ባለቤታቸውን ወ/ሮ ሀናን ጨምሮ የተለያዩ ተቋማትና በመላው ዓለም የሚገኙ ምእመናን ላደረጉት ተሳትፎ ምስጋናቸውን አቅርበዋል ።
በተለይም አቶ ስማቸው ከበደ በሆቴላቸው መርሐ ግብሩ በነጻ እንዲከናወን ከአምስት ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት ነጻ አገልግሎት መስጠታቸው እና የገንዘብ ድጋፍ ማድረጋቸውን ገልጸው ለሌሎች ባለሀብቶችም አርአያነታቸው የጎላ መሆኑን ገልጸዋል።
ደብሩ ገቢ የተደረገውን እና በቃል ኪዳን ሰነድ ቃል የተገባውን ገንዘብ በመሰብሰብ በአጭር ጊዜ ቀሪውን የማጠናቀቂያ ሥራ ፈጽሞ ሕንጻ ቤተመቅደሱን ወደ አገልግሎት ለማስገባት የሕንጻ አሠሪ ኮሚቴው በሥራ ላይ መሆኑን ገልጸዋል ።
የለቡ ምሥራቀ ፀሐይ ቅዱስ ገብርኤል እና መርጡለ ቅድስት አርሴማ ወአቡነ አዳም ገዳም በ1986 ዓ.ም የተመሠረተ ደብር ነው።
ኹነቱን በበጎ አድራጎት ያስተባበረው ሎዛ ኹነቶች አዘጋጅ መኾኑን የገዳሙ አስተዳዳሪ መልአከ ጽዮን ቆሞስ አባ እስጢፋኖስ ይርጋ ተናግረው ለሚዲያዎች፣ ለአገልጋዮች እና ለምእመናን ምስጋናቸውን አቅርበዋል
1 month ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) ማክሰኞ ጁን 30 በደቡብ አፍሪካ በተካሄደው ሀገር አቀፍ የጸረ-ስደተኞች ዘመቻ፣ በ'ግሬተር ኦውድትሾርን' አካባቢ መጠነኛ ረብሻ ቢታይም፣ ፖሊስ ሊከሰት የሚችለውን ሁከት ለመከላከል ከፍተኛ ጥበቃ አድርጓል።
ህገ-ወጥ የተባሉ ስደተኞችን ኢላማ አድርጎ በተካሄደው በዚህ ዘመቻ፣ የውጭ ዜጎች ባለቤት የሆኑባቸው በርካታ አነስተኛ ሱቆች ለጥንቃቄ ሲባል በጊዜያዊነት የተዘጉ ሲሆን፣ በኦውድትሾርን እና በዳይሰልስዶርፕ የፖሊስ አባላት ዝርፊያን እና ህዝባዊ ረብሻን ለመከላከል በስፋት ተሰማርተዋል።
ካለፈው ሳምንት ጀምሮ በአካባቢው ህገ-ወጥ ስደተኛ ናቸው ተብለው የተጠረጠሩ የተለያዩ ሀገራት ዜጎች መታሰራቸው ተዘግቧል። የፖሊስ ቃል አቀባይ ሌተና ኮሎኔል ማልኮም ፖጂ፣ እስካሁን የተያዙትን ሰዎች ትክክለኛ ቁጥር ከመናገር የተቆጠቡ ሲሆን፣ "የተጠናቀረ ሪፖርት በሀገር አቀፍ ፖሊስ በኩል ወደፊት ይፋ ይደረጋል" ብለዋል። ይሁን እንጂ 'ኦውድትሾርን ኩራንት' ከተዓማኒ ምንጮች እንዳገኘው መረጃ፣ ካለፈው ዓርብ ጀምሮ በርካታ የውጭ ዜጎች ታስረዋል። በተጨማሪም፣ በዳይሰልስዶርፕ የውጭ ዜጎችን ሱቆች ዘርፈዋል የተባሉ ሁለት የአካባቢው ነዋሪዎችም በንግድ ተቋም ዝርፊያ ወንጀል ተይዘዋል።
ይህ ህገ-ወጥ ስደተኞችን የማደን ዘመቻ በአካባቢው ማህበረሰብ ዘንድ የተለያየ ምላሽ ፈጥሯል። የውጭ ዜጎች ሱቆች በብዛት በሚገኙባቸው ሰፈሮች የሚኖሩ ሰዎች፣ እነዚህ ሱቆች በተመጣጣኝ ዋጋ ምግብ እና አስፈላጊ ቁሳቁሶችን በማቅረብ ጠቃሚ ሚና እንዳላቸው ገልጸዋል። በ'ሮዝ ቫሊ' የሚገኙ በርካታ ነዋሪዎች ሱቆቹ በጊዜያዊነት መዘጋታቸው ስጋት እንደፈጠረባቸው ተናግረዋል።
"በእነዚህ ሱቆች አንድ ዳቦ በ10 ራንድ ፣ ስኳር ደግሞ በ2 ራንድ መግዛት እንችላለን። ትላልቅ ሱቆች ጋር ይህን ማድረግ አንችልም፤ ደግሞም ከምንኖርበት አካባቢ በጣም የራቁ ናቸው። ለትራንስፖርት የሚሆን ገንዘብም የለንም" ሲል አንድ ነዋሪ ቅሬታውን ገልጿል። በኒው ሉክ እና ቦንጎሌቱ በሚገኝ አንድ የውጭ ዜጋ ሱቅ ላይ፣ የአካባቢው ነዋሪዎች ዝርፊያ ሲጀምሩ ፖሊስ ጣልቃ ገብቶ ማስቆሙም ተነግሯል።
ጋዜጣው ለ13 ዓመታት በደቡብ አፍሪካ ከኖሩት እና በኦውድትሾርን ከተማ የሁለት ሱቆች ባለቤት ከሆኑት የኢትዮጵያውያን ማህበረሰብ መሪ አለማየሁ ሎዳሞ (አሌክስ) ጋር ቆይታ አድርጓል። አለማየሁ ከጎንደር ዩኒቨርሲቲ በአካባቢ ጤና አጠባበቅ የመጀመሪያ ዲግሪ አላቸው።
እንደ እሳቸው ገለጻ፣ በረብሻው ወቅት በኦውድትሾርን የሚገኙ አራት የውጭ ዜጎች ሱቆች የተዘረፉ ሲሆን፣ ሁለቱ ደግሞ በዳይሰልስዶርፕ ይገኛሉ። አንድ የሱቅ ባለቤት በድንጋይ ተመትቶ መቁሰሉንም ተናግረው፣ እነዚህ ክስተቶች ለፖሊስ ሪፖርት መደረጋቸውን አስታውቀዋል።
"ሆኖም የአካባቢው ነዋሪዎች ዘራፊዎቹን ለማስቆም እና ሱቆቻችንን ለመጠበቅ ጥረት አድርገዋል፤ ለዚህም በጣም እናመሰግናቸዋለን" ብለዋል።
አለማየሁ አክለውም በአካባቢው የሚኖሩ በርካታ ኢትዮጵያውያን በሀገራቸው ካለው ግጭት እና ጦርነት ሸሽተው ደህንነት እና የተሻለ ህይወት ፍለጋ በስደተኛነት ወደ ደቡብ አፍሪካ የገቡ መሆናቸውን አብራርተዋል። የስደተኞች ፈቃድ በአብዛኛው በአምስት የስደተኞች መቀበያ ጽሕፈት ቤቶች ብቻ የሚታደስ በመሆኑ፣ ብዙ ሰዎች ረጅም ርቀት ለመጓዝ እንደሚገደዱ ገልጸዋል። ከኮቪድ-19 ወረርሽኝ በኋላ አንዳንድ የእድሳት ሂደቶች በበይነመረብ ቢገኙም፣ አሰራሩ እጅግ የዘገየ እና አሰልቺ መሆኑን፣ አመልካቾችም ሰነዶቻቸውን ለማሳደስ ለረጅም ጊዜ እንደሚጠብቁ አስረድተዋል።
"ወደ ደቡብ አፍሪካ የምንመጣው ለራሳችን እና ለቤተሰቦቻችን የተሻለ የወደፊት ህይወት እና ደህንነቱ የተጠበቀ መኖሪያ ፈልገን ነው፤ ባዶ እጃችንን እና የምንሄድበት ጠፍቶን ነው የመጣነው። እኔ የዩኒቨርሲቲ ዲግሪ አለኝ፣ ለኢትዮጵያ መንግስትም ሰርቻለሁ፤ ነገር ግን የደቡብ አፍሪካ ዜጋ ስላልሆንኩ ትምህርቴን ልጠቀምበት አልቻልኩም" ሲሉ በሀዘን ተናግረዋል።
ከሌሎች ሀገራት በተለየ ደቡብ አፍሪካ ስደተኞችን በመደበኛ የስደተኞች መጠለያ ካምፕ ውስጥ እንደማታስቀምጥ የገለጹት አለማየሁ፣ "በዚህ ምክንያት ብዙዎቻችን እንደ አንሶላ እና መጋረጃ ያሉ ዕቃዎችን ቤት ለቤት በመሸጥ እንጀምራለን። በቂ ገንዘብ ስናጠራቅም ደግሞ ቤተሰቦቻችንን ለማስተዳደር ትናንሽ ሱቆችን እንከፍታለን። እንደ ዝርፊያ ያሉ የወንጀል ድርጊቶች በእኛ ላይ እጅግ አውዳሚ የሆነ የገንዘብ ቀውስ ይፈጥራሉ" ብለዋል።
በደቡብ አፍሪካ የሚገኙ አብዛኛዎቹ የውጭ ሀገር ማህበረሰቦች፣ አባሎቻቸው የደቡብ አፍሪካን ህግ እንዲያከብሩ የሚያበረታቱ ማህበረሰብ መሪዎች እንደሚመርጡም ተናግረዋል። "ወገኖቻችን የዚህን ሀገር ህግ እንዲያከብሩ እንሰራለን። በወንጀል ድርጊቶች የሚሳተፉ ህገ-ወጥ ስደተኞች መኖራቸውን አንክድም፤ ነገር ግን እነሱ ሁላችንንም አይወክሉም፣ ድርጊታቸውንም አንደግፍም። አንድ ሰው ወንጀል ከሰራ፣ እስራትም ሆነ መባረር፣ የሚገባውን ቅጣት ማግኘት አለበት። እኛ ሰላማዊ ህይወት ለመኖር እና ዘር ወይም ዜግነት ሳንለይ ለሁሉም ሰው አክብሮት ለማሳየት እንሞክራለን" በማለት ማብራሪያቸውን አጠናቀዋል።
ህገ-ወጥ የተባሉ ስደተኞችን ኢላማ አድርጎ በተካሄደው በዚህ ዘመቻ፣ የውጭ ዜጎች ባለቤት የሆኑባቸው በርካታ አነስተኛ ሱቆች ለጥንቃቄ ሲባል በጊዜያዊነት የተዘጉ ሲሆን፣ በኦውድትሾርን እና በዳይሰልስዶርፕ የፖሊስ አባላት ዝርፊያን እና ህዝባዊ ረብሻን ለመከላከል በስፋት ተሰማርተዋል።
ካለፈው ሳምንት ጀምሮ በአካባቢው ህገ-ወጥ ስደተኛ ናቸው ተብለው የተጠረጠሩ የተለያዩ ሀገራት ዜጎች መታሰራቸው ተዘግቧል። የፖሊስ ቃል አቀባይ ሌተና ኮሎኔል ማልኮም ፖጂ፣ እስካሁን የተያዙትን ሰዎች ትክክለኛ ቁጥር ከመናገር የተቆጠቡ ሲሆን፣ "የተጠናቀረ ሪፖርት በሀገር አቀፍ ፖሊስ በኩል ወደፊት ይፋ ይደረጋል" ብለዋል። ይሁን እንጂ 'ኦውድትሾርን ኩራንት' ከተዓማኒ ምንጮች እንዳገኘው መረጃ፣ ካለፈው ዓርብ ጀምሮ በርካታ የውጭ ዜጎች ታስረዋል። በተጨማሪም፣ በዳይሰልስዶርፕ የውጭ ዜጎችን ሱቆች ዘርፈዋል የተባሉ ሁለት የአካባቢው ነዋሪዎችም በንግድ ተቋም ዝርፊያ ወንጀል ተይዘዋል።
ይህ ህገ-ወጥ ስደተኞችን የማደን ዘመቻ በአካባቢው ማህበረሰብ ዘንድ የተለያየ ምላሽ ፈጥሯል። የውጭ ዜጎች ሱቆች በብዛት በሚገኙባቸው ሰፈሮች የሚኖሩ ሰዎች፣ እነዚህ ሱቆች በተመጣጣኝ ዋጋ ምግብ እና አስፈላጊ ቁሳቁሶችን በማቅረብ ጠቃሚ ሚና እንዳላቸው ገልጸዋል። በ'ሮዝ ቫሊ' የሚገኙ በርካታ ነዋሪዎች ሱቆቹ በጊዜያዊነት መዘጋታቸው ስጋት እንደፈጠረባቸው ተናግረዋል።
"በእነዚህ ሱቆች አንድ ዳቦ በ10 ራንድ ፣ ስኳር ደግሞ በ2 ራንድ መግዛት እንችላለን። ትላልቅ ሱቆች ጋር ይህን ማድረግ አንችልም፤ ደግሞም ከምንኖርበት አካባቢ በጣም የራቁ ናቸው። ለትራንስፖርት የሚሆን ገንዘብም የለንም" ሲል አንድ ነዋሪ ቅሬታውን ገልጿል። በኒው ሉክ እና ቦንጎሌቱ በሚገኝ አንድ የውጭ ዜጋ ሱቅ ላይ፣ የአካባቢው ነዋሪዎች ዝርፊያ ሲጀምሩ ፖሊስ ጣልቃ ገብቶ ማስቆሙም ተነግሯል።
ጋዜጣው ለ13 ዓመታት በደቡብ አፍሪካ ከኖሩት እና በኦውድትሾርን ከተማ የሁለት ሱቆች ባለቤት ከሆኑት የኢትዮጵያውያን ማህበረሰብ መሪ አለማየሁ ሎዳሞ (አሌክስ) ጋር ቆይታ አድርጓል። አለማየሁ ከጎንደር ዩኒቨርሲቲ በአካባቢ ጤና አጠባበቅ የመጀመሪያ ዲግሪ አላቸው።
እንደ እሳቸው ገለጻ፣ በረብሻው ወቅት በኦውድትሾርን የሚገኙ አራት የውጭ ዜጎች ሱቆች የተዘረፉ ሲሆን፣ ሁለቱ ደግሞ በዳይሰልስዶርፕ ይገኛሉ። አንድ የሱቅ ባለቤት በድንጋይ ተመትቶ መቁሰሉንም ተናግረው፣ እነዚህ ክስተቶች ለፖሊስ ሪፖርት መደረጋቸውን አስታውቀዋል።
"ሆኖም የአካባቢው ነዋሪዎች ዘራፊዎቹን ለማስቆም እና ሱቆቻችንን ለመጠበቅ ጥረት አድርገዋል፤ ለዚህም በጣም እናመሰግናቸዋለን" ብለዋል።
አለማየሁ አክለውም በአካባቢው የሚኖሩ በርካታ ኢትዮጵያውያን በሀገራቸው ካለው ግጭት እና ጦርነት ሸሽተው ደህንነት እና የተሻለ ህይወት ፍለጋ በስደተኛነት ወደ ደቡብ አፍሪካ የገቡ መሆናቸውን አብራርተዋል። የስደተኞች ፈቃድ በአብዛኛው በአምስት የስደተኞች መቀበያ ጽሕፈት ቤቶች ብቻ የሚታደስ በመሆኑ፣ ብዙ ሰዎች ረጅም ርቀት ለመጓዝ እንደሚገደዱ ገልጸዋል። ከኮቪድ-19 ወረርሽኝ በኋላ አንዳንድ የእድሳት ሂደቶች በበይነመረብ ቢገኙም፣ አሰራሩ እጅግ የዘገየ እና አሰልቺ መሆኑን፣ አመልካቾችም ሰነዶቻቸውን ለማሳደስ ለረጅም ጊዜ እንደሚጠብቁ አስረድተዋል።
"ወደ ደቡብ አፍሪካ የምንመጣው ለራሳችን እና ለቤተሰቦቻችን የተሻለ የወደፊት ህይወት እና ደህንነቱ የተጠበቀ መኖሪያ ፈልገን ነው፤ ባዶ እጃችንን እና የምንሄድበት ጠፍቶን ነው የመጣነው። እኔ የዩኒቨርሲቲ ዲግሪ አለኝ፣ ለኢትዮጵያ መንግስትም ሰርቻለሁ፤ ነገር ግን የደቡብ አፍሪካ ዜጋ ስላልሆንኩ ትምህርቴን ልጠቀምበት አልቻልኩም" ሲሉ በሀዘን ተናግረዋል።
ከሌሎች ሀገራት በተለየ ደቡብ አፍሪካ ስደተኞችን በመደበኛ የስደተኞች መጠለያ ካምፕ ውስጥ እንደማታስቀምጥ የገለጹት አለማየሁ፣ "በዚህ ምክንያት ብዙዎቻችን እንደ አንሶላ እና መጋረጃ ያሉ ዕቃዎችን ቤት ለቤት በመሸጥ እንጀምራለን። በቂ ገንዘብ ስናጠራቅም ደግሞ ቤተሰቦቻችንን ለማስተዳደር ትናንሽ ሱቆችን እንከፍታለን። እንደ ዝርፊያ ያሉ የወንጀል ድርጊቶች በእኛ ላይ እጅግ አውዳሚ የሆነ የገንዘብ ቀውስ ይፈጥራሉ" ብለዋል።
በደቡብ አፍሪካ የሚገኙ አብዛኛዎቹ የውጭ ሀገር ማህበረሰቦች፣ አባሎቻቸው የደቡብ አፍሪካን ህግ እንዲያከብሩ የሚያበረታቱ ማህበረሰብ መሪዎች እንደሚመርጡም ተናግረዋል። "ወገኖቻችን የዚህን ሀገር ህግ እንዲያከብሩ እንሰራለን። በወንጀል ድርጊቶች የሚሳተፉ ህገ-ወጥ ስደተኞች መኖራቸውን አንክድም፤ ነገር ግን እነሱ ሁላችንንም አይወክሉም፣ ድርጊታቸውንም አንደግፍም። አንድ ሰው ወንጀል ከሰራ፣ እስራትም ሆነ መባረር፣ የሚገባውን ቅጣት ማግኘት አለበት። እኛ ሰላማዊ ህይወት ለመኖር እና ዘር ወይም ዜግነት ሳንለይ ለሁሉም ሰው አክብሮት ለማሳየት እንሞክራለን" በማለት ማብራሪያቸውን አጠናቀዋል።
Sponsored by
Surafel
2 months ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ባለፈው አንድ ወር ውስጥ የሀገሪቱ ወታደራዊ ኃይል በሆርሙዝ የባህር ሰላጤ ላይ እጅግ ስኬታማ የነበረ "ስውር ተልዕኮ" ማከናወኑን በይፋ ገለጹ። ፕሬዝዳንቱ ቀደም ሲል በኦቫል ኦፊስ የሰጡትን መግለጫ በማብራራት "ትሩዝ ሶሻል" በተሰኘው የማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት፣ የአሜሪካ ጦር የነዳጅ ጫኝ እና ሌሎች የንግድ መርከቦችን በሰላጤው በሰላም ለማሳለፍ ትልቅ ስውር ኦፕሬሽን ሲያካሂድ መቆየቱን ይፋ አድርገዋል።
ትራምፕ በመልዕክታቸው "በዚህ ስውር ጥረት አማካኝነት ከ100 ሚሊዮን በርሜል በላይ ነዳጅ የሆርሙዝን የባህር ሰላጤ በሰላም አቋርጦ ወደ ዓለም አቀፉ ገበያ እንዲገባ መደረጉን ለመግለጽ እወዳለሁ" ብለዋል። አክለውም በዚህ ሂደት ውስጥ ከ200 በላይ የንግድ መርከቦች ያለምንም የደህንነት ስጋት ቀጠናውን ማቋረጣቸውን ጠቅሰው፣ "ይህ እጅግ ታላቅ ስኬት ሊመዘገብ የቻለው የሆርሙዝን የባህር ሰላጤ የሚቆጣጠረው ዩናይትድ ስቴትስ ኦፍ አሜሪካ እንጂ ኢራን ስላልሆነች ነው" ሲሉ ለቴህራን ጠንካራ መልዕክት አስተላልፈዋል።
ፕሬዝዳንት ትራምፕ ቀደም ሲል በሰጡት መግለጫ... የአሜሪካ ጦር በምሽት አጋማሽ በሚያደርገው ስውር ኦፕሬሽን በሚሊዮን የሚቆጠር በርሜል ነዳጅ ከአካባቢው እያስወጣ መሆኑንና ኢራንም ይህንን ልታውቅ እንዳልቻለች ተናግረው ነበር። ለዚህም እንደ ምክንያት የጠቀሱት፣ ቀደም ሲል አሜሪካ በሰነዘረችው የአየር ጥቃት የኢራን የራዳር መከላከያ ሥርዓቶች ሙሉ በሙሉ መውደማቸውን ነው።
ይህ የፕሬዝዳንት ትራምፕ መግለጫ አሜሪካ በመካከለኛው ምስራቅ ባለው ቁልፍ የነዳጅ ማስተላለፊያ መስመር ላይ ያላትን ወታደራዊ የበላይነት በይፋ ለማሳየት እና የዓለምን የነዳጅ ገበያ ለማረጋጋት ያለመ የፖለቲካ ድል አዋጅ ነው። ሆኖም "የሆርሙዝን ሰላጤ አሜሪካ እንጂ ኢራን አትቆጣጠረውም" የሚለው የትራምፕ የሀይል ንግግር፣ ዓለም አቀፍ የባህር ላይ ሕጎችን እና የኢራንን ቀጣናዊ ይገባኛል ጥያቄ በቀጥታ የሚጋፋ በመሆኑ ፍጥጫውን ይበልጥ ሊያፋፍመው ይችላል። በተጨማሪም፣ ይህ መግለጫ የመጣው የነዳጅ ዋጋ በከፍተኛ ሁኔታ በናረበት እና የአሜሪካ አክሲዮን ገበያ በወረደበት ወቅት መሆኑ፣ ትራምፕ የውስጥ የፖለቲካ እና የኢኮኖሚ ጫናዎችን ለመቀነስ የጦርነት ድሎችን የፕሮፓጋንዳ መሣሪያ እያደረጓቸው ነው የሚለውን የምሁራን ስጋት ያጠናክራል።
ትራምፕ በመልዕክታቸው "በዚህ ስውር ጥረት አማካኝነት ከ100 ሚሊዮን በርሜል በላይ ነዳጅ የሆርሙዝን የባህር ሰላጤ በሰላም አቋርጦ ወደ ዓለም አቀፉ ገበያ እንዲገባ መደረጉን ለመግለጽ እወዳለሁ" ብለዋል። አክለውም በዚህ ሂደት ውስጥ ከ200 በላይ የንግድ መርከቦች ያለምንም የደህንነት ስጋት ቀጠናውን ማቋረጣቸውን ጠቅሰው፣ "ይህ እጅግ ታላቅ ስኬት ሊመዘገብ የቻለው የሆርሙዝን የባህር ሰላጤ የሚቆጣጠረው ዩናይትድ ስቴትስ ኦፍ አሜሪካ እንጂ ኢራን ስላልሆነች ነው" ሲሉ ለቴህራን ጠንካራ መልዕክት አስተላልፈዋል።
ፕሬዝዳንት ትራምፕ ቀደም ሲል በሰጡት መግለጫ... የአሜሪካ ጦር በምሽት አጋማሽ በሚያደርገው ስውር ኦፕሬሽን በሚሊዮን የሚቆጠር በርሜል ነዳጅ ከአካባቢው እያስወጣ መሆኑንና ኢራንም ይህንን ልታውቅ እንዳልቻለች ተናግረው ነበር። ለዚህም እንደ ምክንያት የጠቀሱት፣ ቀደም ሲል አሜሪካ በሰነዘረችው የአየር ጥቃት የኢራን የራዳር መከላከያ ሥርዓቶች ሙሉ በሙሉ መውደማቸውን ነው።
ይህ የፕሬዝዳንት ትራምፕ መግለጫ አሜሪካ በመካከለኛው ምስራቅ ባለው ቁልፍ የነዳጅ ማስተላለፊያ መስመር ላይ ያላትን ወታደራዊ የበላይነት በይፋ ለማሳየት እና የዓለምን የነዳጅ ገበያ ለማረጋጋት ያለመ የፖለቲካ ድል አዋጅ ነው። ሆኖም "የሆርሙዝን ሰላጤ አሜሪካ እንጂ ኢራን አትቆጣጠረውም" የሚለው የትራምፕ የሀይል ንግግር፣ ዓለም አቀፍ የባህር ላይ ሕጎችን እና የኢራንን ቀጣናዊ ይገባኛል ጥያቄ በቀጥታ የሚጋፋ በመሆኑ ፍጥጫውን ይበልጥ ሊያፋፍመው ይችላል። በተጨማሪም፣ ይህ መግለጫ የመጣው የነዳጅ ዋጋ በከፍተኛ ሁኔታ በናረበት እና የአሜሪካ አክሲዮን ገበያ በወረደበት ወቅት መሆኑ፣ ትራምፕ የውስጥ የፖለቲካ እና የኢኮኖሚ ጫናዎችን ለመቀነስ የጦርነት ድሎችን የፕሮፓጋንዳ መሣሪያ እያደረጓቸው ነው የሚለውን የምሁራን ስጋት ያጠናክራል።
2 months ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) በአለም ዋንጫ የሚሳተፉት የኢራን ብሄራዊ ቡድን ተጨዋቾች የተሰጣቸው የአሜሪካ ቪዛ የ1 ቀን መሆኑ ተሰማ፡፡ በ2026 አለም ዋንጫ የሚሳተፈው የኢራን ብሄራዊ ቡድን የአሜሪካ መግቢያ ቪዛ እንደተሰጠው መገለፁ ይታወሳል፡፡ ይህንን ተከትሎ የብሄራዊ ቡድኑን አባላት የጫነው አውሮፕላን ዛሬ በሜክሲኮ ድንበር የሚገኘው ቲጁአና ከተማ አርፏል፡፡ አውሮፕላኑ ከቱርክ ተነስቶ ስፔን ጥቂት ቆይታ ካደረገ በኋላ እዚህች ከተማ ያረፈው በውድድሩ ወቅት ዋና ካምፑን እዚያው ለማድረግ በማቀድ ነው፡፡
በሜክሲኮ፣ አሜሪካና ካናዳ የጋራ አዘጋጅነት በሚከናወነው የዘንድሮው አለም ዋንጫ የኢራን ቡድን ሁሉንም የምድብ ማጣሪያ ግጥሚያዎቹን በአሜሪካ እንደሚያደርግ ይታወቃል፡፡ ብሄራዊ ቡድኑ ጨዋታዎቹ በካናዳ ወይንም በሜክሲኮ እንዲሆኑለት ጥያቄ ቢያቀርብም በፊፋ ተቀባይነት ባለማግኘቱ ከቤልጂየምና ከኒውዚላንድ ጋር በሎስ አንጀለስ እንዲሁም ከግብፅ ጋር በሲያትል ጨዋታውን የሚያካሂድ ይሆናል፡፡ ነገር ግን በሜክሲኮ የሚገኙት የኢራን አምባሳደር ዛሬ እንደገለፁት ለብሄራዊ ቡድኑ አባላት የተሰጠው ቪዛ ‹‹ገብቶ የመውጣት›› የአንድ ቀን መሆኑን አስታውቀዋል፡፡
አምባሳደሩ እንደሚሉት ተጨዋቾቹ በግጥሚያቸው እለት ከሜክሲኮዋ ቲጁአና ከተማ ተነስተው ወደአሜሪካ ስታዲየም የመጓዝ ቪዛ አላቸው፡፡ ይህ ቪዛ ግን ልክ የጨዋታው መጠናቀቅን የሚያበስረው ፊሽካ ሲሰማ የሚጠናቀቅ ይሆናል፡፡ በመሆኑም በጨዋታ እለት ተነስተው ወደአሜሪካ በመጓዝ ተመልሰው ወደሜክሲኮ ለመጓዝ እንደሚገደዱ አስታውቀዋል፡፡ ይህ መግለጫቸው ከዚህ ቀደም የኢራን እግርኳስ ፌዴሬሽን ቃል አቀባይ ከተናገሩት ጋር የሚቃረን ነው፡፡ ቃል አቀባዩ በንግግራቸው ተጨዋቾቹ በመጀመሪያው ግጥሚያ ከአንድ ቀን ቀደም ብለው አሜሪካ እንደሚገቡና በተከታይ ባሉት ሁለት ግጥሚያዎች ግን እለት 2 ቀን ቀደም ብለው ለመግባት የሚስችል ቪዛ እንደተሰጣቸው ተናግረው ነበር፡፡ ይ
ህ በእንዲህ እንዳለ የኢራን እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዝደንቱ ማህዲ ታጅ ዛሬ በሰጡት መግለጫ ለብሄራዊ ቡድኑ ተጨዋቾች የተጠቀሰው ቪዛ ቢሰጥም 15 ለሚሆኑ የቡድኑ አባላት ግን ቪዛ መከልከሉን ገልፀዋል፡፡ ይህም አግባብ አለመሆኑን አስታውቀዋል፡፡ በተያያዘ አሜሪካና ኢራን ከየምድባቸው ሁለተኛ ሆነው የሚያጠናቅቁ ከሆነ በቀጣይ እርስ በእርሳቸው እንደሚጋጠሙ የወጣው መርሀ ግብር ያሳያል፡፡ በመርሀ ግብሩ መሰረት ሁለቱም ከምድባቸው 2ተኛ ሆነው ካጠናቀቁ ግጥሚያቸው ጁላይ 3 ቀን በቴክሳስ አርሊንግተን ይሆናል፡፡
በሜክሲኮ፣ አሜሪካና ካናዳ የጋራ አዘጋጅነት በሚከናወነው የዘንድሮው አለም ዋንጫ የኢራን ቡድን ሁሉንም የምድብ ማጣሪያ ግጥሚያዎቹን በአሜሪካ እንደሚያደርግ ይታወቃል፡፡ ብሄራዊ ቡድኑ ጨዋታዎቹ በካናዳ ወይንም በሜክሲኮ እንዲሆኑለት ጥያቄ ቢያቀርብም በፊፋ ተቀባይነት ባለማግኘቱ ከቤልጂየምና ከኒውዚላንድ ጋር በሎስ አንጀለስ እንዲሁም ከግብፅ ጋር በሲያትል ጨዋታውን የሚያካሂድ ይሆናል፡፡ ነገር ግን በሜክሲኮ የሚገኙት የኢራን አምባሳደር ዛሬ እንደገለፁት ለብሄራዊ ቡድኑ አባላት የተሰጠው ቪዛ ‹‹ገብቶ የመውጣት›› የአንድ ቀን መሆኑን አስታውቀዋል፡፡
አምባሳደሩ እንደሚሉት ተጨዋቾቹ በግጥሚያቸው እለት ከሜክሲኮዋ ቲጁአና ከተማ ተነስተው ወደአሜሪካ ስታዲየም የመጓዝ ቪዛ አላቸው፡፡ ይህ ቪዛ ግን ልክ የጨዋታው መጠናቀቅን የሚያበስረው ፊሽካ ሲሰማ የሚጠናቀቅ ይሆናል፡፡ በመሆኑም በጨዋታ እለት ተነስተው ወደአሜሪካ በመጓዝ ተመልሰው ወደሜክሲኮ ለመጓዝ እንደሚገደዱ አስታውቀዋል፡፡ ይህ መግለጫቸው ከዚህ ቀደም የኢራን እግርኳስ ፌዴሬሽን ቃል አቀባይ ከተናገሩት ጋር የሚቃረን ነው፡፡ ቃል አቀባዩ በንግግራቸው ተጨዋቾቹ በመጀመሪያው ግጥሚያ ከአንድ ቀን ቀደም ብለው አሜሪካ እንደሚገቡና በተከታይ ባሉት ሁለት ግጥሚያዎች ግን እለት 2 ቀን ቀደም ብለው ለመግባት የሚስችል ቪዛ እንደተሰጣቸው ተናግረው ነበር፡፡ ይ
ህ በእንዲህ እንዳለ የኢራን እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዝደንቱ ማህዲ ታጅ ዛሬ በሰጡት መግለጫ ለብሄራዊ ቡድኑ ተጨዋቾች የተጠቀሰው ቪዛ ቢሰጥም 15 ለሚሆኑ የቡድኑ አባላት ግን ቪዛ መከልከሉን ገልፀዋል፡፡ ይህም አግባብ አለመሆኑን አስታውቀዋል፡፡ በተያያዘ አሜሪካና ኢራን ከየምድባቸው ሁለተኛ ሆነው የሚያጠናቅቁ ከሆነ በቀጣይ እርስ በእርሳቸው እንደሚጋጠሙ የወጣው መርሀ ግብር ያሳያል፡፡ በመርሀ ግብሩ መሰረት ሁለቱም ከምድባቸው 2ተኛ ሆነው ካጠናቀቁ ግጥሚያቸው ጁላይ 3 ቀን በቴክሳስ አርሊንግተን ይሆናል፡፡
2 months ago
በተግባር የተገለጠው የጠቅላይ ሚኒስትሩ ቃል - አዲስ አበባን የማዘመን ጉዞ ስኬት
**********************
ጥቅምት 12 ቀን 2016 ዓ.ም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) "የዛሬ አምስት ዓመት አዲስ አበባ በአፍሪካ ውስጥ እጅግ ውብ ከሚባሉ ከተሞች አንዷ ትሆናለች" ሲሉ ተናግረው ነበር።
ያኔ ንግግራቸውን ከሰሙት መካከል የመዲናዋን የዛሬ ገጽታ በዐይነ ኅሊናቸው የሣሉት ጥቂቶች ነበሩ።
በወቅቱ ንግግሩ ከተራ የፖለቲካ ተስፋ በላይ ትርጉም አይኖረውም ብለው የተጠራጠሩ ቢኖሩም፣ ዛሬ ግን አዲስ አበባ በአጭር ጊዜ ውስጥ እጅግ ማራኪ፣ ጽዱ እና ዘመናዊ ዲፕሎማሲያዊ ማዕከል በመሆን ራዕዩን በተግባር አሳይታለች።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በመዲናዋ ተበታትነው የሚገኙትን እምቅ አቅሞች ወይም "ያልተያያዙ ትላልቅ ዶቶችን" በማገናኘት ከተማዋን በአዲስ መልክ የመገንባት ዕቅድ እንዳላቸው አስረድተውም ነበር።
ይህ አርቆ አሳቢ የከተማ ልማት ፍልስፍና ታሪካዊ ክስተቶችን የሚያስታውስ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትሩ እንዳስታወሱት፣ ንጉሥ ላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናትን መገንባት በጀመሩበት ወቅት "ድንጋይ መቆርቆር የስንፍና ምልክት ነው" በማለት ያሾፉባቸው ነበሩ።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ፈጣሪዎች እና አልሚዎች ሁልጊዜም በዘመናቸው ካሉ "አውርቶ አደር" ተቺዎች ጋር መጋፈጣቸው አይቀርም የሚል እሳቤ አላቸው።
ዛሬ በኮሪደር ልማቱ እየታየ ያለውም ይኸው እውነታ ነው፤ "እኛ የምንሠራው ለዛሬ ብቻ ሳይሆን ለነገ እና ለቀጣዩ ትውልድ ነው፤ ነገ የሚፈርስ ዳስ አንሠራም" በሚለው መርሐቸው ለትውልድ የሚሻገር ዘላቂ ሥራ እየተሠራ ይገኛል።
"የመደመር መንግሥት" መጽሐፍ ላይ እንደተብራራው፣ ከተሜነት የብልጽግና መዳረሻ እና የኢኮኖሚ ሞተር ነው።
ከተማን ማዘመን ረጃጅም ሕንፃዎችን ከመገንባት ባለፈ ሰፊ የእግረኛ እና የሳይክል መንገዶችን፣ አረንጓዴ ስፍራዎችን እና ምቹ መሠረተ ልማቶችን ማካተትን ይጠይቃል።
አዲስ አበባ ላይ በተግባር ሥራ ላይ ውሎ አዲስ አበባን ምርጥ የአፍሪካ ከተማ ያደረገው ይኸው ሰዎችን ማዕከል ያደረገው ፍልስፍና ነው።
ከዚህ ቀደም የተገነቡት አንድነት ፓርክ፣ እንጦጦ ፓርክ፣ ወዳጅነት አደባባይ እና የዓድዋ ድል መታሰቢያ የዚህ ዘመናዊ አስተሳሰብ ማሳያዎች ናቸው።
በዚህም የኮሪደር ልማቱ በግንባታው ሂደት ለበርካታ ዜጎች ሰፊ የሥራ ዕድል ከመፍጠሩም በላይ፣ የካርቦን ልቀትን በመቀነስ የነዋሪዎችን ጤና እና ደኅንነት የሚጠብቅ ንፁህ አካባቢን መፍጠር ችሏል።
እነዚህ ስልታዊ ለውጦች አዲስ አበባን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለበርካታ ሽልማቶች አብቅተዋታል።
በ2015 ዓ.ም በናይሮቢ በተካሄደው የአፍሪካ ስማርት ሲቲዎች ኢንቨስትመንት ጉባኤ ላይ 36 የአፍሪካ ከተሞችን በመብለጥ ‘የዓመቱ ምርጥ ስማርት ሲቲ' ሽልማትን አሸንፋለች።
እንዲሁም የተባበሩት መንግሥታት የአፍሪካ አዳራሽ (Historic Africa Hall) እድሳት ፕሮጀክት የሞደርኒዝም ጥበቃ ሽልማትን (World Monuments Fund/Knoll Modernism Prize) ተቀዳጅቷል።
ይህ ሽልማት ከተመሠረተበት እ.ኤ.አ. 2008 ጀምሮ በአፍሪካ አህጉር ሲሰጥ አዲስ አበባ የመጀመሪያዋ ነች።
እነዚህ ስኬቶች ከተማዋ እ.አ.አ በ2027 የዓለም አየር ንብረት ለውጥ ጉባኤን (COP32) እንድታስተናግድ ትልቅ መተማመኛ ፈጥረዋል።
በአዲስ አበባ የተመዘገበው ይህ ስኬታማ የከተማ ማዘመን ልምድ በአሁኑ ወቅት ከ70 በላይ ወደሚሆኑ የሀገራችን ከተሞችም እንዲስፋፋ ተደርጓል።
ይህ አዲስ የከተማ ማሻሻያ ፍልስፍና በቱሪዝም ዘርፉ ላይም ታይቶ የማይታወቅ መነቃቃት ፈጥሯል።
በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያዎቹ ዘጠኝ ወራት ብቻ ከ1.5 ሚሊዮን በላይ ከሚሆኑ የውጭ ቱሪስቶች ከ2.6 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ ተገኝቷል።
በተባበሩት መንግሥታት የቱሪዝም ድርጅት (UN Tourism) መረጃ መሰረትም ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ2025 የዓለም አቀፍ ቱሪስቶችን ፍሰት በ15 በመቶ በማሳደግ ፈጣን ዕድገት እያስመዘገቡ ካሉ የቱሪዝም መዳረሻዎች ተርታ ተሰልፋለች።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ይህን ግዙፍ ልማት ሲያከናውን ያጋጠሙትን ማኅበራዊ እና ሕጋዊ ተግዳሮቶች ሰብአዊነትን በተላበሰ መንገድ ለመፍታት ያደረገው ጥረት የልማቱን ፍትሐዊነት ያረጋግጣል።
ከተማዋን ለሕፃናት፣ ለወጣቶች እና ለአካል ጉዳተኞች ጭምር ምቹ በማድረግ የቦታ ፍትሐዊነትን ማረጋገጥ ተችሏል።
ጥቅምት 12 ቀን 2016 ዓ.ም የተነገረው ራዕይ ዛሬ እውን ሆኖ፣ አዲስ አበባ በምድረ አፍሪካ ውብ፣ ተመራጭ እና የሁሉንም ነዋሪዎቿን ፍላጎት ያማከለች መዲና መሆኗን በተግባር እያረጋገጠች ትገኛለች።
በለሚ ታደሰ
#ethiopia #ebc #addisababa #corridordevelopment #smartcity
**********************
ጥቅምት 12 ቀን 2016 ዓ.ም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) "የዛሬ አምስት ዓመት አዲስ አበባ በአፍሪካ ውስጥ እጅግ ውብ ከሚባሉ ከተሞች አንዷ ትሆናለች" ሲሉ ተናግረው ነበር።
ያኔ ንግግራቸውን ከሰሙት መካከል የመዲናዋን የዛሬ ገጽታ በዐይነ ኅሊናቸው የሣሉት ጥቂቶች ነበሩ።
በወቅቱ ንግግሩ ከተራ የፖለቲካ ተስፋ በላይ ትርጉም አይኖረውም ብለው የተጠራጠሩ ቢኖሩም፣ ዛሬ ግን አዲስ አበባ በአጭር ጊዜ ውስጥ እጅግ ማራኪ፣ ጽዱ እና ዘመናዊ ዲፕሎማሲያዊ ማዕከል በመሆን ራዕዩን በተግባር አሳይታለች።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በመዲናዋ ተበታትነው የሚገኙትን እምቅ አቅሞች ወይም "ያልተያያዙ ትላልቅ ዶቶችን" በማገናኘት ከተማዋን በአዲስ መልክ የመገንባት ዕቅድ እንዳላቸው አስረድተውም ነበር።
ይህ አርቆ አሳቢ የከተማ ልማት ፍልስፍና ታሪካዊ ክስተቶችን የሚያስታውስ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትሩ እንዳስታወሱት፣ ንጉሥ ላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናትን መገንባት በጀመሩበት ወቅት "ድንጋይ መቆርቆር የስንፍና ምልክት ነው" በማለት ያሾፉባቸው ነበሩ።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ፈጣሪዎች እና አልሚዎች ሁልጊዜም በዘመናቸው ካሉ "አውርቶ አደር" ተቺዎች ጋር መጋፈጣቸው አይቀርም የሚል እሳቤ አላቸው።
ዛሬ በኮሪደር ልማቱ እየታየ ያለውም ይኸው እውነታ ነው፤ "እኛ የምንሠራው ለዛሬ ብቻ ሳይሆን ለነገ እና ለቀጣዩ ትውልድ ነው፤ ነገ የሚፈርስ ዳስ አንሠራም" በሚለው መርሐቸው ለትውልድ የሚሻገር ዘላቂ ሥራ እየተሠራ ይገኛል።
"የመደመር መንግሥት" መጽሐፍ ላይ እንደተብራራው፣ ከተሜነት የብልጽግና መዳረሻ እና የኢኮኖሚ ሞተር ነው።
ከተማን ማዘመን ረጃጅም ሕንፃዎችን ከመገንባት ባለፈ ሰፊ የእግረኛ እና የሳይክል መንገዶችን፣ አረንጓዴ ስፍራዎችን እና ምቹ መሠረተ ልማቶችን ማካተትን ይጠይቃል።
አዲስ አበባ ላይ በተግባር ሥራ ላይ ውሎ አዲስ አበባን ምርጥ የአፍሪካ ከተማ ያደረገው ይኸው ሰዎችን ማዕከል ያደረገው ፍልስፍና ነው።
ከዚህ ቀደም የተገነቡት አንድነት ፓርክ፣ እንጦጦ ፓርክ፣ ወዳጅነት አደባባይ እና የዓድዋ ድል መታሰቢያ የዚህ ዘመናዊ አስተሳሰብ ማሳያዎች ናቸው።
በዚህም የኮሪደር ልማቱ በግንባታው ሂደት ለበርካታ ዜጎች ሰፊ የሥራ ዕድል ከመፍጠሩም በላይ፣ የካርቦን ልቀትን በመቀነስ የነዋሪዎችን ጤና እና ደኅንነት የሚጠብቅ ንፁህ አካባቢን መፍጠር ችሏል።
እነዚህ ስልታዊ ለውጦች አዲስ አበባን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለበርካታ ሽልማቶች አብቅተዋታል።
በ2015 ዓ.ም በናይሮቢ በተካሄደው የአፍሪካ ስማርት ሲቲዎች ኢንቨስትመንት ጉባኤ ላይ 36 የአፍሪካ ከተሞችን በመብለጥ ‘የዓመቱ ምርጥ ስማርት ሲቲ' ሽልማትን አሸንፋለች።
እንዲሁም የተባበሩት መንግሥታት የአፍሪካ አዳራሽ (Historic Africa Hall) እድሳት ፕሮጀክት የሞደርኒዝም ጥበቃ ሽልማትን (World Monuments Fund/Knoll Modernism Prize) ተቀዳጅቷል።
ይህ ሽልማት ከተመሠረተበት እ.ኤ.አ. 2008 ጀምሮ በአፍሪካ አህጉር ሲሰጥ አዲስ አበባ የመጀመሪያዋ ነች።
እነዚህ ስኬቶች ከተማዋ እ.አ.አ በ2027 የዓለም አየር ንብረት ለውጥ ጉባኤን (COP32) እንድታስተናግድ ትልቅ መተማመኛ ፈጥረዋል።
በአዲስ አበባ የተመዘገበው ይህ ስኬታማ የከተማ ማዘመን ልምድ በአሁኑ ወቅት ከ70 በላይ ወደሚሆኑ የሀገራችን ከተሞችም እንዲስፋፋ ተደርጓል።
ይህ አዲስ የከተማ ማሻሻያ ፍልስፍና በቱሪዝም ዘርፉ ላይም ታይቶ የማይታወቅ መነቃቃት ፈጥሯል።
በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያዎቹ ዘጠኝ ወራት ብቻ ከ1.5 ሚሊዮን በላይ ከሚሆኑ የውጭ ቱሪስቶች ከ2.6 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ ተገኝቷል።
በተባበሩት መንግሥታት የቱሪዝም ድርጅት (UN Tourism) መረጃ መሰረትም ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ2025 የዓለም አቀፍ ቱሪስቶችን ፍሰት በ15 በመቶ በማሳደግ ፈጣን ዕድገት እያስመዘገቡ ካሉ የቱሪዝም መዳረሻዎች ተርታ ተሰልፋለች።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ይህን ግዙፍ ልማት ሲያከናውን ያጋጠሙትን ማኅበራዊ እና ሕጋዊ ተግዳሮቶች ሰብአዊነትን በተላበሰ መንገድ ለመፍታት ያደረገው ጥረት የልማቱን ፍትሐዊነት ያረጋግጣል።
ከተማዋን ለሕፃናት፣ ለወጣቶች እና ለአካል ጉዳተኞች ጭምር ምቹ በማድረግ የቦታ ፍትሐዊነትን ማረጋገጥ ተችሏል።
ጥቅምት 12 ቀን 2016 ዓ.ም የተነገረው ራዕይ ዛሬ እውን ሆኖ፣ አዲስ አበባ በምድረ አፍሪካ ውብ፣ ተመራጭ እና የሁሉንም ነዋሪዎቿን ፍላጎት ያማከለች መዲና መሆኗን በተግባር እያረጋገጠች ትገኛለች።
በለሚ ታደሰ
#ethiopia #ebc #addisababa #corridordevelopment #smartcity
2 months ago
ራዕይና የህዝብ እምነት
*******
ግንቦት 24/2018 ዓ.ም የሀገሪቱን የቀጣይ አምስት ዓመታት እጣ ፈንታ የሚወስን ሀገራዊ ምርጫ በተካሄደበት ማግስት ግንቦት 25 በማለዳ የሀገሪቱና የአዲስ አበባ ከተማ አመራሮች እንጦጦ ላይ ተከስተው ነበር። ጫና ሳይበግረው ህዝቡ እስከ እኩለ ሌሊት በመጠበቅ ዴሞክራሲያዊ መብቱን ለመተግበር ያሳየውን ቁርጠኝነት በማድነቅ ያመሰገኑት ጠ/ሚ/ር አብይ እና ከንቲባ አዳነች ህዝቡን ለመካስ የጀመሩትን ስራ ለማስቀጠል ሰበብ ፈልገው ጊዜ ማባካን ተገቢ ባለመሆኑ ነው እዛ የተገኙት። በውጤቱም ለከተማዋም ሆነ ለህዝቡ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያለውን የወንዝ ዳርቻ ልማት መርቀው ለአገልግሎት ክፍት አድርገዋል።
በመሰረቱ እነዚህ ሁለቱ መሪዎች ለሚባክን ጊዜ ምንም ጊዜ እንደሌላቸው አብረዋቸው የሰሩ ባልደረቦቻቸውና የስራቸው ውጤት ምስክሮቻቸው ናቸው። ለሚሰሩት ስራ የሰዓት ገደብ የላቸውም፣ ቀን ብቻ ሳይሆን ማታም መደበኛ የስራ ሰዓታቸው ነው። የነበረ አሰራር ከውጤታማነት እንዲጎትታቸው አይፈቅዱም፣ ቀልጣፋና ዘመናዊ አሰራር እውን ማድረግ መርሃቸው ነው። ለጊዜያዊና ወቅታዊ ውዳሴም ሆነ ኩነኔ ጆሮ የላቸውም፣ በምስጋናም ሆነ በእርግማን ከትልቁ መዳረሻቸው እንደማይጎድሉ ተረድተዋል።
እኔ ግን እላችኋለሁ የእነዚህ መሪዎች ትጋት ገፊ ምክንያት ራዕያቸው ነው፣ የእነዚህ መሪዎች ትጋት ገፊ ምክንያት የህዝቡ እምነት ነው። ድህነትን፣ ጉስቁልናን፣ ኋላ ቀርነትን በመፀየፍ፣ የበለፀገችና ተወዳዳሪ ሀገር እውን የማድረግ ራዕይ የትጋታቸው መሰረታዊ ጉልበት ነው። በብዙ እልህ አስጨራሽ ተግዳሮት ውስጥ ቢያልፉም ከስምንት ዓመት በፊት ያዩት እና ዛሬም ህዝቡ በእነርሱ ላይ ያለው የፀና እምነት ለትጋታቸው ተጨማሪ ጉልበት ሆኗቸዋል።
ማህበራዊ ፍትህ የሰፈነባት፣ የበለፀገች፣ ተወዳዳሪና የዜጎችዋ ክብር የተመለሰላት ሀገር እውን እስኪያደርጉ ድረስ እረፍት እንደማይኖራቸው ሰርተው ያመጡት ውጤት ብቻ ሳይሆን ለነገ የሚናገሩት ቃልና የሚገቡት ተስፋ ይመሰክራል። ተናግረው ማድረግን በተግባር ያሳዩ መሆናቸው ደግሞ ራዕያቸውን ለመደገፍና ቃላቸውን ለማመን ምክንያት ይሆናል።
መልዕክት አለኝ:- ራዕያቸው፣ ትጋታቸውና ቁጭታቸው የገባን ቀኝ እጃችንን እንስጣቸው፤ በሌቦች፣ በጽንፈኞችና በስልጣን ጥመኞች ሴራ የተጠራጠርናቸው ደግሞ ረጋ ብለን በስራቸው እንመዝናቸው። ደግሜ የገባኝን እላለሁ እነዚህ መሪዎች መዳረሻቸውን ከመነሻቸው አይተው የተነሱ ናቸውና ራዕያቸውን ሳያሳኩ ለመቆም፣ ለማረፍ፣ ተስፋ ለመቁረጥ ሀሳብም ጊዜም አይኖራቸውም።
ተፃፈ በይመጣል ባህሩ
*******
ግንቦት 24/2018 ዓ.ም የሀገሪቱን የቀጣይ አምስት ዓመታት እጣ ፈንታ የሚወስን ሀገራዊ ምርጫ በተካሄደበት ማግስት ግንቦት 25 በማለዳ የሀገሪቱና የአዲስ አበባ ከተማ አመራሮች እንጦጦ ላይ ተከስተው ነበር። ጫና ሳይበግረው ህዝቡ እስከ እኩለ ሌሊት በመጠበቅ ዴሞክራሲያዊ መብቱን ለመተግበር ያሳየውን ቁርጠኝነት በማድነቅ ያመሰገኑት ጠ/ሚ/ር አብይ እና ከንቲባ አዳነች ህዝቡን ለመካስ የጀመሩትን ስራ ለማስቀጠል ሰበብ ፈልገው ጊዜ ማባካን ተገቢ ባለመሆኑ ነው እዛ የተገኙት። በውጤቱም ለከተማዋም ሆነ ለህዝቡ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያለውን የወንዝ ዳርቻ ልማት መርቀው ለአገልግሎት ክፍት አድርገዋል።
በመሰረቱ እነዚህ ሁለቱ መሪዎች ለሚባክን ጊዜ ምንም ጊዜ እንደሌላቸው አብረዋቸው የሰሩ ባልደረቦቻቸውና የስራቸው ውጤት ምስክሮቻቸው ናቸው። ለሚሰሩት ስራ የሰዓት ገደብ የላቸውም፣ ቀን ብቻ ሳይሆን ማታም መደበኛ የስራ ሰዓታቸው ነው። የነበረ አሰራር ከውጤታማነት እንዲጎትታቸው አይፈቅዱም፣ ቀልጣፋና ዘመናዊ አሰራር እውን ማድረግ መርሃቸው ነው። ለጊዜያዊና ወቅታዊ ውዳሴም ሆነ ኩነኔ ጆሮ የላቸውም፣ በምስጋናም ሆነ በእርግማን ከትልቁ መዳረሻቸው እንደማይጎድሉ ተረድተዋል።
እኔ ግን እላችኋለሁ የእነዚህ መሪዎች ትጋት ገፊ ምክንያት ራዕያቸው ነው፣ የእነዚህ መሪዎች ትጋት ገፊ ምክንያት የህዝቡ እምነት ነው። ድህነትን፣ ጉስቁልናን፣ ኋላ ቀርነትን በመፀየፍ፣ የበለፀገችና ተወዳዳሪ ሀገር እውን የማድረግ ራዕይ የትጋታቸው መሰረታዊ ጉልበት ነው። በብዙ እልህ አስጨራሽ ተግዳሮት ውስጥ ቢያልፉም ከስምንት ዓመት በፊት ያዩት እና ዛሬም ህዝቡ በእነርሱ ላይ ያለው የፀና እምነት ለትጋታቸው ተጨማሪ ጉልበት ሆኗቸዋል።
ማህበራዊ ፍትህ የሰፈነባት፣ የበለፀገች፣ ተወዳዳሪና የዜጎችዋ ክብር የተመለሰላት ሀገር እውን እስኪያደርጉ ድረስ እረፍት እንደማይኖራቸው ሰርተው ያመጡት ውጤት ብቻ ሳይሆን ለነገ የሚናገሩት ቃልና የሚገቡት ተስፋ ይመሰክራል። ተናግረው ማድረግን በተግባር ያሳዩ መሆናቸው ደግሞ ራዕያቸውን ለመደገፍና ቃላቸውን ለማመን ምክንያት ይሆናል።
መልዕክት አለኝ:- ራዕያቸው፣ ትጋታቸውና ቁጭታቸው የገባን ቀኝ እጃችንን እንስጣቸው፤ በሌቦች፣ በጽንፈኞችና በስልጣን ጥመኞች ሴራ የተጠራጠርናቸው ደግሞ ረጋ ብለን በስራቸው እንመዝናቸው። ደግሜ የገባኝን እላለሁ እነዚህ መሪዎች መዳረሻቸውን ከመነሻቸው አይተው የተነሱ ናቸውና ራዕያቸውን ሳያሳኩ ለመቆም፣ ለማረፍ፣ ተስፋ ለመቁረጥ ሀሳብም ጊዜም አይኖራቸውም።
ተፃፈ በይመጣል ባህሩ
2 months ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከኢራን ጋር ሊያደርጉት ነው በተባለው አዲስ ስምምነት ዙሪያ፣ የሪፐብሊካን ፓርቲ ታላላቅ ፖለቲከኞች የተለያየ እና የሚጋጭ አቋም እያንጸባረቁ ይገኛሉ። እስካሁን በይፋ የተደረሰ ስምምነትም ሆነ የወጣ ዝርዝር መረጃ ባይኖርም፣ ሊኖር ይችላል የተባለው ስምምነት በፓርቲው ውስጥ ከፍተኛ ክርክር አስነስቷል።
ታዋቂው ሴኔተር ቴድ ክሩዝ በጉዳዩ ላይ ከፍተኛ ስጋት እንዳደረባቸው ገልጸዋል። ሴኔተሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ላይ ባሰፈሩት ጽሁፍ፣ ትራምፕ በኢራን ላይ ጥቃት መክፈታቸው ትክክለኛ እርምጃ ቢሆንም፣ ስምምነቱ ኢራን በቢሊዮን የሚቆጠር ዶላር እንድታገኝ፣ ዩራኒየም እንድታበለጽግ፣ የኒውክሌር መሳሪያ እንድትሰራ እና የሆርሙዝ ባህረ ሰላጤን እንድትቆጣጠር የሚፈቅድ ከሆነ ግን "አስከፊ ስህተት" ይሆናል በማለት አጥብቀው አስጠንቅቀዋል።
በተመሳሳይ ሴኔተር ቶም ቲሊስ ሂደቱ ትርጉም እንደማይሰጣቸው ተናግረዋል። የመከላከያ ሚኒስትሩ ፒት ሄግሴዝ ከሳምንታት በፊት የኢራን መከላከያ ሙሉ በሙሉ መውደሙን እና የኒውክሌር ማዕድኑን በእጅ ማስገባት የጊዜ ጉዳይ ብቻ መሆኑን ተናግረው እንደነበር ያስታወሱት ሴኔተሩ፣ አሁን ላይ የኒውክሌር ማቴሪያሉ በኢራን ውስጥ ሊቀር እንደሚችል የሚጠቁሙ ሀሳቦች ለምን እንደሚነሱ በጥያቄ አቅርበዋል።
በሌላ በኩል ደግሞ ስምምነቱን በአዎንታዊ መልኩ የሚመለከቱ የፓርቲው አባላት አልጠፉም። ኮንግረስማን ቶማስ ማሲ ለኤንቢሲ (NBC) በሰጡት አስተያየት፣ እንደ ሊንድሴይ ግርሃም እና ቴድ ክሩዝ ያሉ ሴኔተሮች ስምምነቱን አጥብቀው የሚቃወሙት ከሆነ፣ ስምምነቱ "በጣም ጥሩ" ሊሆን እንደሚችል ተናግረዋል።
ኮንግረስማን ማሲ ባለፈው ዓመት የአሜሪካ ጦር ያለ ኮንግረሱ ፈቃድ በኢራን ላይ ወታደራዊ እርምጃ እንዳይወስድ የሚከለክል የውሳኔ ሀሳብ አቅርበው እንደነበር ይታወሳል።
እንዲሁም የሴኔቱ አብላጫ ድምጽ አስተባባሪ የሆኑት ጆን ባራሶ፣ የስምምነቱ ዝርዝር ሁኔታ ገና ባይታወቅም፣ የትራምፕ የሀይል እርምጃ እና የአሜሪካ ጥንካሬ ኢራንን ተገዳ ወደ ድርድር ጠረጴዛ እንድትመጣ አድርጓታል በማለት ለሂደቱ ያላቸውን አዎንታዊ አቋም አንጸባርቀዋል።
ታዋቂው ሴኔተር ቴድ ክሩዝ በጉዳዩ ላይ ከፍተኛ ስጋት እንዳደረባቸው ገልጸዋል። ሴኔተሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ላይ ባሰፈሩት ጽሁፍ፣ ትራምፕ በኢራን ላይ ጥቃት መክፈታቸው ትክክለኛ እርምጃ ቢሆንም፣ ስምምነቱ ኢራን በቢሊዮን የሚቆጠር ዶላር እንድታገኝ፣ ዩራኒየም እንድታበለጽግ፣ የኒውክሌር መሳሪያ እንድትሰራ እና የሆርሙዝ ባህረ ሰላጤን እንድትቆጣጠር የሚፈቅድ ከሆነ ግን "አስከፊ ስህተት" ይሆናል በማለት አጥብቀው አስጠንቅቀዋል።
በተመሳሳይ ሴኔተር ቶም ቲሊስ ሂደቱ ትርጉም እንደማይሰጣቸው ተናግረዋል። የመከላከያ ሚኒስትሩ ፒት ሄግሴዝ ከሳምንታት በፊት የኢራን መከላከያ ሙሉ በሙሉ መውደሙን እና የኒውክሌር ማዕድኑን በእጅ ማስገባት የጊዜ ጉዳይ ብቻ መሆኑን ተናግረው እንደነበር ያስታወሱት ሴኔተሩ፣ አሁን ላይ የኒውክሌር ማቴሪያሉ በኢራን ውስጥ ሊቀር እንደሚችል የሚጠቁሙ ሀሳቦች ለምን እንደሚነሱ በጥያቄ አቅርበዋል።
በሌላ በኩል ደግሞ ስምምነቱን በአዎንታዊ መልኩ የሚመለከቱ የፓርቲው አባላት አልጠፉም። ኮንግረስማን ቶማስ ማሲ ለኤንቢሲ (NBC) በሰጡት አስተያየት፣ እንደ ሊንድሴይ ግርሃም እና ቴድ ክሩዝ ያሉ ሴኔተሮች ስምምነቱን አጥብቀው የሚቃወሙት ከሆነ፣ ስምምነቱ "በጣም ጥሩ" ሊሆን እንደሚችል ተናግረዋል።
ኮንግረስማን ማሲ ባለፈው ዓመት የአሜሪካ ጦር ያለ ኮንግረሱ ፈቃድ በኢራን ላይ ወታደራዊ እርምጃ እንዳይወስድ የሚከለክል የውሳኔ ሀሳብ አቅርበው እንደነበር ይታወሳል።
እንዲሁም የሴኔቱ አብላጫ ድምጽ አስተባባሪ የሆኑት ጆን ባራሶ፣ የስምምነቱ ዝርዝር ሁኔታ ገና ባይታወቅም፣ የትራምፕ የሀይል እርምጃ እና የአሜሪካ ጥንካሬ ኢራንን ተገዳ ወደ ድርድር ጠረጴዛ እንድትመጣ አድርጓታል በማለት ለሂደቱ ያላቸውን አዎንታዊ አቋም አንጸባርቀዋል።
3 months ago
ኢራን በጦርነቱ ለደረሰባት ውድመት ካሳ እንዲሁም የአሜሪካ ወታደሮች እንዲወጡ የሚጠይቅ ሃሳብ አቀረበች
ኢራን በሁሉም ግንባሮች የተከፈቱ ጦርነቶች እንዲቆሙ እና ለደረሰባት ጉዳት ካሳ እንዲከፈላት የሚጠይቅ የስምምነት ሃሳብ አቀረበች።
አዲሱ የሰላም ዕቅድ በሊባኖስ ውስጥ የሚካሄደውን ጨምሮ በሁሉም ግንባሮች የሚደረጉ ጦርነቶች እንዲቆሙ፣ በኢራን አቅራቢያ የሰፈሩ የአሜሪካ ወታደሮች እንዲወጡ እና በጦርነቱ ለደረሰባት ውድመት ካሳን እንዲከፈላት የሚጠይቅ መሆኑን የአገሪቱ መገናኛ ብዙኃን ዘግበዋል።
ቴህራን የሰላም ዕቅዱን በሚመለከት በሰጠችው የመጀመሪያ አስተያየት ምክትል ውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ካዘም ጋሪባባዲ ማዕቀቦች እንዲነሱ፣ እንዳይንቀሳቀሱ የታገዱ ንብረቶቿ እንዲለቀቁ አንዲሁም የአሜሪካ ባሕር ኃይል የጣለውን እገዳ እንዲያነሳ መጠየቃቸውን ኢርና የዜና ወኪል ዘግቧል።
የኢራን መገናኛ ብዙኃን እንደዘገቡት ከሆነ የቴህራን አዲሱ ዕቅድ ከዚህ በፊት ካቀረበችው እና የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ “ቆሻሻ” ሲሉ ውደቅ ካደረጉት ብዙም የተለየ አይደለም።
ትራምፕ ሰኞ ዕለት አቅደውት የነበረውን ጥቃት ያቆሙት ቴህራን ለዋሺንግተን አዲስ ሰላም ዕቅድ መላኳን ተከትሎ መሆኑን ተናግረው፤ የኢራንን የኒውክሌር ፕሮግራም ለመገደብ እና ከስምምነት ላይ ለመድረስ “በጣም ጥሩ ዕድል አለ” ብለዋል።
ትራምፕ በማኅበራዊ ሚዲያ ልጥፋቸው ላይ ኳታር፣ ሳዑዲ አረቢያ እና ዩናይትድ አረብ ኤሜሬትስ “አሜሪካ እንዲሁም የመካከለኛው ምሥራቅ አገራት ሊቀበሉት የሚችሉት ስምምነት ላይ ሊደረስ ይችላል” በማለት ጥቃቱ እንዲዘገይ መጠየቃቸውን ተናግረዋል።
ዶናልድ ትራምፕ ሰኞ ዕለት ቴህራን የኒውክሌር የጦር መሣሪያ እንዳታገኝ የሚያደርግ ስምምነት ላይ መድረስ ከተቻለ ደስተኛ እንደሚሆኑ ተናግረዋል።
BBC
ኢራን በሁሉም ግንባሮች የተከፈቱ ጦርነቶች እንዲቆሙ እና ለደረሰባት ጉዳት ካሳ እንዲከፈላት የሚጠይቅ የስምምነት ሃሳብ አቀረበች።
አዲሱ የሰላም ዕቅድ በሊባኖስ ውስጥ የሚካሄደውን ጨምሮ በሁሉም ግንባሮች የሚደረጉ ጦርነቶች እንዲቆሙ፣ በኢራን አቅራቢያ የሰፈሩ የአሜሪካ ወታደሮች እንዲወጡ እና በጦርነቱ ለደረሰባት ውድመት ካሳን እንዲከፈላት የሚጠይቅ መሆኑን የአገሪቱ መገናኛ ብዙኃን ዘግበዋል።
ቴህራን የሰላም ዕቅዱን በሚመለከት በሰጠችው የመጀመሪያ አስተያየት ምክትል ውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ካዘም ጋሪባባዲ ማዕቀቦች እንዲነሱ፣ እንዳይንቀሳቀሱ የታገዱ ንብረቶቿ እንዲለቀቁ አንዲሁም የአሜሪካ ባሕር ኃይል የጣለውን እገዳ እንዲያነሳ መጠየቃቸውን ኢርና የዜና ወኪል ዘግቧል።
የኢራን መገናኛ ብዙኃን እንደዘገቡት ከሆነ የቴህራን አዲሱ ዕቅድ ከዚህ በፊት ካቀረበችው እና የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ “ቆሻሻ” ሲሉ ውደቅ ካደረጉት ብዙም የተለየ አይደለም።
ትራምፕ ሰኞ ዕለት አቅደውት የነበረውን ጥቃት ያቆሙት ቴህራን ለዋሺንግተን አዲስ ሰላም ዕቅድ መላኳን ተከትሎ መሆኑን ተናግረው፤ የኢራንን የኒውክሌር ፕሮግራም ለመገደብ እና ከስምምነት ላይ ለመድረስ “በጣም ጥሩ ዕድል አለ” ብለዋል።
ትራምፕ በማኅበራዊ ሚዲያ ልጥፋቸው ላይ ኳታር፣ ሳዑዲ አረቢያ እና ዩናይትድ አረብ ኤሜሬትስ “አሜሪካ እንዲሁም የመካከለኛው ምሥራቅ አገራት ሊቀበሉት የሚችሉት ስምምነት ላይ ሊደረስ ይችላል” በማለት ጥቃቱ እንዲዘገይ መጠየቃቸውን ተናግረዋል።
ዶናልድ ትራምፕ ሰኞ ዕለት ቴህራን የኒውክሌር የጦር መሣሪያ እንዳታገኝ የሚያደርግ ስምምነት ላይ መድረስ ከተቻለ ደስተኛ እንደሚሆኑ ተናግረዋል።
BBC
3 months ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በኢራን ጦርነት ምክንያት ተራዝሞ ከነበረው እና በከፍተኛ ጉጉት ከሚጠበቀው የቻይናው ፕሬዝዳንት ሺ ጂንፒንግ ጋር ለሚያደርጉት ስብሰባ ዛሬ ማክሰኞ ወደ ቻይና ያቀናሉ። ምንም እንኳን የንግድ ጉዳይ በሁለቱ መሪዎች መካከል ዋናው የመወያያ አጀንዳ እንደሚሆን ቢጠበቅም፣ በኢራን ያለው አሳሳቢ ሁኔታ እና በፋርስ ባህረ ሰላጤ የተፈጠረው የአቅርቦት ሰንሰለት መስተጓጎል ግን የውይይቱ አስገዳጅ አካል እንደሚሆኑ ፕሬዝዳንቱ ትላንት ሰኞ ተናግረዋል። ከዚህም በተጨማሪ የኃይል (ኢነርጂ) እና የታይዋን ጉዳዮች ላይ እንደሚመክሩ አሳውቀዋል። ቻይና በበኩሏ የአሜሪካን ጣልቃ ገብነት ሳያስፈልግ ታይዋንን ሙሉ በሙሉ በቁጥጥሯ ስር ለማድረግ እየሰራች ትገኛለች።
ከጉዞው አስቀድሞ ትራምፕ ለሺ ጂንፒንግ ያላቸውን ከፍተኛ አድናቆት ገልጸዋል። "እሳቸው ታላቅ እና እጅግ አስገራሚ ሰው ናቸው፤ ከፕሬዝዳንት ሺ ጋር በጣም ጥሩ ግንኙነት አለኝ። ብዙ የንግድ ስራዎችን በጋራ እየሰራን ብዙ ገንዘብ እያገኘን ነው" ሲሉ ባለፈው ሳምንት በኦቫል ኦፊስ ለጋዜጠኞች ተናግረው ነበር። በትሩዝ ሶሻል ገጻቸው ላይም ሺ ሲገናኙ "ትልቅ እቅፍ" እንደሚያደርጓቸው ጽፈው ነበር። ከትራምፕ ጋር ወደ ቤጂንግ ከሚያመሩት ልዑካን መካከል እንደ ኤሎን ማስክ፣ የኤፕል ዋና ስራ አስፈፃሚ ቲም ኩክ፣ የብላክሮክ ላሪ ፊንክ እና የጎልድማን ሳክስ ዴቪድ ሰለሞንን የመሳሰሉ ታላላቅ የንግድ መሪዎች ሊካተቱ እንደሚችሉ ከዋይት ሀውስ የወጡ መረጃዎች ያሳያሉ።
የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ባለሙያዎች እንደሚሉት፣ ሁለቱም ሀገራት ግንኙነታቸው የተረጋጋ እንዲሆን ይፈልጋሉ፤ ይህንንም ለማደፍረስ የትኛውም ወገን ፍላጎት የለውም። በውጭ ግንኙነት ምክር ቤት የቻይና ጉዳዮች ከፍተኛ ተመራማሪ የሆኑት ዞንግዩዋን ዞዪ ሊዩ፣ "ዋናው ስጋታቸው የአሜሪካ እና የቻይና ግንኙነትን እንዴት ማረጋጋት እንደሚቻል ነው። ይህ ደግሞ ሁለቱ ወገኖች ወደ ወታደራዊ ግጭት ሳያመሩ ለረጅም ጊዜ ስትራቴጂካዊ ውድድር ውስጥ መቆየት እንዲችሉ ለማድረግ ነው" ብለዋል።
በስልት እና ዓለም አቀፍ ጥናት ማዕከል የቻይና ጉዳዮች ከፍተኛ ተመራማሪ ሄንሪዬታ ሌቪን እንደሚሉት፣ ቻይና የኢራን ጦርነት ከመጀመሩ በፊትም ቢሆን ከአሜሪካ ጋር ሲነጻጸር ጠንካራ አቋም ላይ እንዳለች ታምን ነበር። "ቻይናውያን የ2025ቱን የንግድ ጦርነት እንዳሸነፉ ይሰማቸዋል፤ አሁን በኢራን ያለው ጦርነት ደግሞ በራስ መተማመናቸውን በተወሰነ ደረጃ ጨምሮታል። አሜሪካ በእስያ ከነበራት ትኩረት ወጥታ በእስያ ጥቃት ለመከላከል በጣም አስፈላጊ የሆኑትን የጦር መሳሪያ ክምችቶች እያሟጠጠች መሆኑን ቻይና አይታለች" ሲሉ አስረድተዋል።
ትራምፕ ባለፈው ሳምንት ቻይና አብዛኛውን የነዳጅ ፍላጎቷን ከሆርሙዝ ስትሬት (የሆርሙዝ የባህር ወሽመጥ) እንደምታገኝ በመጥቀስ፣ ፕሬዝዳንት ሺ ስለዚህ ጉዳይ "በጣም ጥሩ" እንደሆኑ ገልጸዋል። የኮንግረሱ የአሜሪካ እና ቻይና የኢኮኖሚ እና ደህንነት ግምገማ ኮሚሽን መረጃ እንደሚያሳየው፣ ቻይና 90 በመቶ የሚሆነውን የኢራን ኤክስፖርት ነዳጅ በመግዛት ለኢራን ኢኮኖሚ ትልቁን ድጋፍ ታደርጋለች። ይሁን እንጂ ቻይና በኢራን ጉዳይ አሜሪካን መርዳት እንደምትፈልግ በይፋ ያሳየችው ነገር የለም። ፕሬዝዳንቱ ወደ ቻይና ከማቅናታቸው ጥቂት ቀደም ብሎ የአሜሪካ የገንዘብ ሚኒስቴር በበርካታ የቻይና ኩባንያዎች ላይ አዲስ የኢራን ማዕቀቦችን መጣሉን ተከትሎ፣ ቻይና እነዚህን ድርጅቶች እንደምትጠብቅ አስጠንቅቃለች።
የ2025ቱ የንግድ ጦርነት ጋብ ቢልም፣ ንግድ አሁንም የውይይቱ ዋነኛ ርዕስ እንደሚሆን ይጠበቃል። አሜሪካ ፈጣን እና ጠባብ የንግድ ስምምነቶችን (ፕሬዝዳንቱ በትሩዝ ሶሻል ሊያስታውቋቸው የሚችሏቸውን) ስትፈልግ፣ ቻይና ግን የ21ኛውን ክፍለ ዘመን የእስያን የወደፊት እጣ ፈንታ በሚቀርፁ ሰፋ ያሉ ስትራቴጂካዊ ጉዳዮች ላይ ትኩረት አድርጋለች።
ታይዋንን በተመለከተ ትራምፕ፣ "እኔ ከማነሳው በላይ ፕሬዝዳንት ሺ ጉዳዩን እንደሚያነሱት አስባለሁ" ብለዋል። ቻይና አሜሪካ ታይዋንን የቻይና አካል አድርጋ እንድትቀበል ለማሳመን ተስፋ ታደርጋለች። ሌቪን እንዳስገነዘቡት፣ ታይዋን የዘመናዊው ዓለም አቀፍ ኢኮኖሚ በተለይም የሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) እና የሴሚኮንዳክተር ቴክኖሎጂ መሰረት በመሆኗ ለአሜሪካ እጅግ አስፈላጊ ናት። ከዚህም ባለፈ፣ አሜሪካ የታይዋንን ሁኔታ የምትይዝበት መንገድ ለእስያ እና ለአውሮፓ አጋሮቿ ያላትን ቁርጠኝነት የሚያሳይ ትልቅ ፈተና እንደሆነም ተንታኞች አክለው ገልጸዋል።
ከጉዞው አስቀድሞ ትራምፕ ለሺ ጂንፒንግ ያላቸውን ከፍተኛ አድናቆት ገልጸዋል። "እሳቸው ታላቅ እና እጅግ አስገራሚ ሰው ናቸው፤ ከፕሬዝዳንት ሺ ጋር በጣም ጥሩ ግንኙነት አለኝ። ብዙ የንግድ ስራዎችን በጋራ እየሰራን ብዙ ገንዘብ እያገኘን ነው" ሲሉ ባለፈው ሳምንት በኦቫል ኦፊስ ለጋዜጠኞች ተናግረው ነበር። በትሩዝ ሶሻል ገጻቸው ላይም ሺ ሲገናኙ "ትልቅ እቅፍ" እንደሚያደርጓቸው ጽፈው ነበር። ከትራምፕ ጋር ወደ ቤጂንግ ከሚያመሩት ልዑካን መካከል እንደ ኤሎን ማስክ፣ የኤፕል ዋና ስራ አስፈፃሚ ቲም ኩክ፣ የብላክሮክ ላሪ ፊንክ እና የጎልድማን ሳክስ ዴቪድ ሰለሞንን የመሳሰሉ ታላላቅ የንግድ መሪዎች ሊካተቱ እንደሚችሉ ከዋይት ሀውስ የወጡ መረጃዎች ያሳያሉ።
የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ባለሙያዎች እንደሚሉት፣ ሁለቱም ሀገራት ግንኙነታቸው የተረጋጋ እንዲሆን ይፈልጋሉ፤ ይህንንም ለማደፍረስ የትኛውም ወገን ፍላጎት የለውም። በውጭ ግንኙነት ምክር ቤት የቻይና ጉዳዮች ከፍተኛ ተመራማሪ የሆኑት ዞንግዩዋን ዞዪ ሊዩ፣ "ዋናው ስጋታቸው የአሜሪካ እና የቻይና ግንኙነትን እንዴት ማረጋጋት እንደሚቻል ነው። ይህ ደግሞ ሁለቱ ወገኖች ወደ ወታደራዊ ግጭት ሳያመሩ ለረጅም ጊዜ ስትራቴጂካዊ ውድድር ውስጥ መቆየት እንዲችሉ ለማድረግ ነው" ብለዋል።
በስልት እና ዓለም አቀፍ ጥናት ማዕከል የቻይና ጉዳዮች ከፍተኛ ተመራማሪ ሄንሪዬታ ሌቪን እንደሚሉት፣ ቻይና የኢራን ጦርነት ከመጀመሩ በፊትም ቢሆን ከአሜሪካ ጋር ሲነጻጸር ጠንካራ አቋም ላይ እንዳለች ታምን ነበር። "ቻይናውያን የ2025ቱን የንግድ ጦርነት እንዳሸነፉ ይሰማቸዋል፤ አሁን በኢራን ያለው ጦርነት ደግሞ በራስ መተማመናቸውን በተወሰነ ደረጃ ጨምሮታል። አሜሪካ በእስያ ከነበራት ትኩረት ወጥታ በእስያ ጥቃት ለመከላከል በጣም አስፈላጊ የሆኑትን የጦር መሳሪያ ክምችቶች እያሟጠጠች መሆኑን ቻይና አይታለች" ሲሉ አስረድተዋል።
ትራምፕ ባለፈው ሳምንት ቻይና አብዛኛውን የነዳጅ ፍላጎቷን ከሆርሙዝ ስትሬት (የሆርሙዝ የባህር ወሽመጥ) እንደምታገኝ በመጥቀስ፣ ፕሬዝዳንት ሺ ስለዚህ ጉዳይ "በጣም ጥሩ" እንደሆኑ ገልጸዋል። የኮንግረሱ የአሜሪካ እና ቻይና የኢኮኖሚ እና ደህንነት ግምገማ ኮሚሽን መረጃ እንደሚያሳየው፣ ቻይና 90 በመቶ የሚሆነውን የኢራን ኤክስፖርት ነዳጅ በመግዛት ለኢራን ኢኮኖሚ ትልቁን ድጋፍ ታደርጋለች። ይሁን እንጂ ቻይና በኢራን ጉዳይ አሜሪካን መርዳት እንደምትፈልግ በይፋ ያሳየችው ነገር የለም። ፕሬዝዳንቱ ወደ ቻይና ከማቅናታቸው ጥቂት ቀደም ብሎ የአሜሪካ የገንዘብ ሚኒስቴር በበርካታ የቻይና ኩባንያዎች ላይ አዲስ የኢራን ማዕቀቦችን መጣሉን ተከትሎ፣ ቻይና እነዚህን ድርጅቶች እንደምትጠብቅ አስጠንቅቃለች።
የ2025ቱ የንግድ ጦርነት ጋብ ቢልም፣ ንግድ አሁንም የውይይቱ ዋነኛ ርዕስ እንደሚሆን ይጠበቃል። አሜሪካ ፈጣን እና ጠባብ የንግድ ስምምነቶችን (ፕሬዝዳንቱ በትሩዝ ሶሻል ሊያስታውቋቸው የሚችሏቸውን) ስትፈልግ፣ ቻይና ግን የ21ኛውን ክፍለ ዘመን የእስያን የወደፊት እጣ ፈንታ በሚቀርፁ ሰፋ ያሉ ስትራቴጂካዊ ጉዳዮች ላይ ትኩረት አድርጋለች።
ታይዋንን በተመለከተ ትራምፕ፣ "እኔ ከማነሳው በላይ ፕሬዝዳንት ሺ ጉዳዩን እንደሚያነሱት አስባለሁ" ብለዋል። ቻይና አሜሪካ ታይዋንን የቻይና አካል አድርጋ እንድትቀበል ለማሳመን ተስፋ ታደርጋለች። ሌቪን እንዳስገነዘቡት፣ ታይዋን የዘመናዊው ዓለም አቀፍ ኢኮኖሚ በተለይም የሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) እና የሴሚኮንዳክተር ቴክኖሎጂ መሰረት በመሆኗ ለአሜሪካ እጅግ አስፈላጊ ናት። ከዚህም ባለፈ፣ አሜሪካ የታይዋንን ሁኔታ የምትይዝበት መንገድ ለእስያ እና ለአውሮፓ አጋሮቿ ያላትን ቁርጠኝነት የሚያሳይ ትልቅ ፈተና እንደሆነም ተንታኞች አክለው ገልጸዋል።
3 months ago
ኢራን በዓለም ዋንጫ ላይ ለሚኖራት ተሳትፎ ዋስትና ጠየቀች
ኢራን በዓለም ዋንጫ ላይ እንደምትሳፍ ገልጻ ነገር ግን ከፊፋ እና ጨዋታውን ከሚያስተናግዱ አገራት ዋስትና እንደምትፈልግ አስታወቀች።
የኢራን እግር ኳስ ፌዴሬሽን በዓለም ዋንጫ ላይ “ከምናምንብት፣ ከባሕላችን እና ከቁርጠንነታችን ሳናፈገፍግ” እንሳተፋለን ሲሉ አረጋግጠው፣ አዘጋጅ አገራት “ስጋታችንን ከግምት ውስጥ እንዲያስገቡልን እንፈልጋለን” ብለዋል።
የእግር ኳስ ፌዴሬሽኑ መሟላት አለባቸው ያላቸውን ነገሮች ያቀረበው ፕሬዚዳንቱ መሃዲ ታጅ ባለፈው ወር ካናዳ በተካሄደው የፊፋ ጉባዔ ላይ ለመገኘት ሲጠይቁ ቪዛ በመከልከላቸው ነው።
ታጅ አገራቸው በዓለም ዋንጫ ላይ ለመሳተፍ መሟላት አለባቸው ያሏቸውን ባለ አስር ነጥብ ቅድመ ሁኔታዎችን ለፊፋ ማቅረቧን ተናግረዋል።
የዓለም ዋንጫ በሜክሲኮ በካናዳ እና በዩናይትድ ስቴትስ አዘጋጅነት ከሰኔ 4 2018 ዓ.ም. ጀምሮ ይካሄዳል።
ቅዳሜ ዕለት በመግለጫው ላይ ከሰፈሩት ቅድመ ሁኔታዎች መካከል ሁሉም በእስላማዊ አብዮታዊ ዘብ ወታደራዊ ስልጠና ያጠናቀቁትን ጨምሮ ከቡድኑ ጋር የሚጓዙ አሰልጣኞች፣ ተጫዋቾች እና ባለሥልጣናት ቪዛ እንዲሰጣቸው የሚጠይቅ ነው።
የኢራን አብዮታዊ ዘብ በካናዳ እና አሜሪካ አሸባሪ ድርጅት ተብሎ የተፈረጀ ሲሆን፣ መሃዲ ታጂ ወደ ካናዳ መግቢያ ቪዛ የተከለከሉት ከወታደራዊው ተቋሙ ጋር ባላቸው ግንኙነት ነው ተብሏል።
ኢራን ለእግር ኳስ ቡድኗ፣ ለባንዲራዋ እንዲሁም ለብሔራዊ መዝሙሯ ተገቢው ክብር አንዲሰጥ እንዲሁም በአውሮፕላን ማረፊያዎች፣ ሆቴሎች እና ስታዲየሞች ጥበቃ እንዲጠናከርላት ጠይቃለች።
የተወሰኑት የኢራን ጥያቄዎች ፊፋ በቀላሉ እንዲሟሉ ሊያደርጋቸው የሚችላቸው ናቸው።
ነገር ግን ከቪዛ፣ የድንበር ቁጥጥር እና ደህንነት ጋር የተያያዙ ጥያቄዎችን ከፊፋ ይልቅ የአገራቱ ሕግ ስር የሚወድቁ ናቸው።
የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ የኢራን የእግር ኳስ ቡድን መትቶ በዓለም ዋንጫ ላይ ቢካፈል ደስተኛ መሆናቸውን ተናግረው ነበር።
ነገር ግን ከአብዮታዊ ዘቡ ጋር ግንኙነት ያላቸው አባላት ክልከላ እንደሚገጥማቸው አስጠንቅቀዋል።
BBC
ኢራን በዓለም ዋንጫ ላይ እንደምትሳፍ ገልጻ ነገር ግን ከፊፋ እና ጨዋታውን ከሚያስተናግዱ አገራት ዋስትና እንደምትፈልግ አስታወቀች።
የኢራን እግር ኳስ ፌዴሬሽን በዓለም ዋንጫ ላይ “ከምናምንብት፣ ከባሕላችን እና ከቁርጠንነታችን ሳናፈገፍግ” እንሳተፋለን ሲሉ አረጋግጠው፣ አዘጋጅ አገራት “ስጋታችንን ከግምት ውስጥ እንዲያስገቡልን እንፈልጋለን” ብለዋል።
የእግር ኳስ ፌዴሬሽኑ መሟላት አለባቸው ያላቸውን ነገሮች ያቀረበው ፕሬዚዳንቱ መሃዲ ታጅ ባለፈው ወር ካናዳ በተካሄደው የፊፋ ጉባዔ ላይ ለመገኘት ሲጠይቁ ቪዛ በመከልከላቸው ነው።
ታጅ አገራቸው በዓለም ዋንጫ ላይ ለመሳተፍ መሟላት አለባቸው ያሏቸውን ባለ አስር ነጥብ ቅድመ ሁኔታዎችን ለፊፋ ማቅረቧን ተናግረዋል።
የዓለም ዋንጫ በሜክሲኮ በካናዳ እና በዩናይትድ ስቴትስ አዘጋጅነት ከሰኔ 4 2018 ዓ.ም. ጀምሮ ይካሄዳል።
ቅዳሜ ዕለት በመግለጫው ላይ ከሰፈሩት ቅድመ ሁኔታዎች መካከል ሁሉም በእስላማዊ አብዮታዊ ዘብ ወታደራዊ ስልጠና ያጠናቀቁትን ጨምሮ ከቡድኑ ጋር የሚጓዙ አሰልጣኞች፣ ተጫዋቾች እና ባለሥልጣናት ቪዛ እንዲሰጣቸው የሚጠይቅ ነው።
የኢራን አብዮታዊ ዘብ በካናዳ እና አሜሪካ አሸባሪ ድርጅት ተብሎ የተፈረጀ ሲሆን፣ መሃዲ ታጂ ወደ ካናዳ መግቢያ ቪዛ የተከለከሉት ከወታደራዊው ተቋሙ ጋር ባላቸው ግንኙነት ነው ተብሏል።
ኢራን ለእግር ኳስ ቡድኗ፣ ለባንዲራዋ እንዲሁም ለብሔራዊ መዝሙሯ ተገቢው ክብር አንዲሰጥ እንዲሁም በአውሮፕላን ማረፊያዎች፣ ሆቴሎች እና ስታዲየሞች ጥበቃ እንዲጠናከርላት ጠይቃለች።
የተወሰኑት የኢራን ጥያቄዎች ፊፋ በቀላሉ እንዲሟሉ ሊያደርጋቸው የሚችላቸው ናቸው።
ነገር ግን ከቪዛ፣ የድንበር ቁጥጥር እና ደህንነት ጋር የተያያዙ ጥያቄዎችን ከፊፋ ይልቅ የአገራቱ ሕግ ስር የሚወድቁ ናቸው።
የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ የኢራን የእግር ኳስ ቡድን መትቶ በዓለም ዋንጫ ላይ ቢካፈል ደስተኛ መሆናቸውን ተናግረው ነበር።
ነገር ግን ከአብዮታዊ ዘቡ ጋር ግንኙነት ያላቸው አባላት ክልከላ እንደሚገጥማቸው አስጠንቅቀዋል።
BBC
3 months ago
የዩክሬን ግጭት 'እየተጠናቀቀ ነው' ብለው እንደሚያስቡ ፑቲን ተናገሩ
ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን አገራቸው ከዩክሬን ጋር እያካሄደች ያለችው ጦርነት እያበቃ ነው ብለው እንደሚያስቡ ተናገሩ።
ፕሬዚዳንቱ ይህንን ያሉት ሶቪየት ኅብረት ናዚ ጀርመንን ድል ያደረገችበትን በዓል ካከበረች በኋላ ከጋዜጠኞች ጋር በነበራቸው ቆይታ ወቅት ነው።
"ጉዳዩ እየተጠናቀቀ ነው ብዬ አስባለሁ" ሲሉ በዩክሬን እየተካሄደ ስለሚገኘው "ልዩ ወታደራዊ ዘመቻ" ተናግረው ምዕራባውያን ለኪዬቭ መንግሥትን የሚያደርጉትን ድጋፍ ኮንነዋል።
የሩሲያ ዓመታዊ የድል በዓል ዩክሬን በቀዩ አደባባይ በድሮኖች ጥቃት ልታደርስ ትችላለች በሚል ስጋት የተለመደውን የታንክ እና የሚሳኤል ሠልፍ አላካሄዱም።
የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በመጨረሻ ደቂቃ ባደራደሩት እና በሞስኮ እና በኪየቭ መካከል በተደረገ የተኩስ አቁም ስምምነት የጥቃት ስጋቱ ቀንሶ ሠልፉ ያለ ምንም አደጋ ተጠናቋል።
ፑቲን አስተያየትቱን የሰጡት የድል ቀን ንግግራቸውን ጦርነቱን ምክንያታዊነት ለማረጋገጥ ከተጠቀሙ ከጥቂት ሰዓታት በኋላ ነው።
በንግግራቸውም ሩሲያ "ፍትሃዊ" ጦርነት እየተዋጋች እንደሆነ እና ዩክሬንን "በኔቶ የሚታጠቀ እና የሚደገፍ ጠበኛ ኃይል" ብለው ጠርተዋታል።
ምዕራባውያን ዩክሬንን ስለመርዳታቸው በተመለከተ በጋዜጣዊ መግለጫ ወቅት የተጠየቁት ፑቲን "እርዳታ ቃል ገብተው እስከ ዛሬ ድረስም ከሩሲያ ጋር ግጭቱን ማቀጣጠል ጀመሩ። ጉዳዩ እያበቃ ነው ብዬ ባስብም ግን ከባድ ጉዳይ ነው" ሲሉ ምላሽ ሰጥተዋል።
የሩሲያ ኃይሎች በ2014 ክሬሚያን እና የምሥራቅ ዩክሬን ክፍሎችን የተቆጣጠሩ ሲሆን እአአ በየካቲት 2022 የዩክሬን ሙሉ ወረራን ጀመሩ።
ፑቲን የዩክሬን ፕሬዝዳንት ቮሎዲሚር ዜሌንስኪን የሚያገኙት ዘላቂ የሰላም ስምምነት ከተደረሰ በኋላ ብቻ እንደሆነ ተናግረዋል።
"በሦስተኛ አገር መገናኘትም ቢቻልም ግን በዚህ ዝግጅት ላይ ለመሳተፍ እና ለመፈረም የረዥም ጊዜ ታሪካዊ እይታን ለመፍጠር የሰላም ስምምነት ላይ የመጨረሻ ስምምነቶች ከተደረሱ በኋላ ብቻ ነው። ይህም የመጨረሻ እርምጃ መሆን አለበት" ሲሉ አክለዋል።
ዜሌንስኪ በግል ሊያገኟቸው ዝግጁ መሆናቸውን ቢሰሙም "እንዲህ አይነት መግለጫዎችን ስንሰማ ይህ የመጀመሪያ ጊዜ አይደለም" ብለዋል ፑቲን።
ፑቲን ለአውሮፓ አዲስ የደህንነት ስምምነቶችን ለመደራደር ፈቃደኛ እንደሆኑ እና የሚመርጡት የድርድር አጋር የጀርመን የቀድሞ ቻንስለር ጄርሃርድ ሽሮደር እንደሆኑ ጠቅሰዋል።
የቀድሞው ቻንስለር የፑቲን የረዠም ጊዜ ወዳጅ ሲሆኑ በሩሲያ መንግሥት ባለቤትነት ስር ላሉ የኤነርጂ ኩባንያዎች ላይ በመሥራታቸው ምክንያት አወዛጋቢ ናቸው።
ባለፈው ሳምንት የአውሮፓ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት አንቶኒዮ ኮስታ የአውሮፓ ኅብረት ከሩሲያ ጋር ለመደራደር "ተስፋ" እንዳለው እና ዜሌንስኪ እንዲህ ዓይነት እርምጃን እንደሚደግፉ እንደሚያምኑ ተናግረዋል።
በፋይናንሺያል ታይምስ በተጠቀሰው የኮስታ ንግግር መሠረት የአውሮፓ ኅብረት መሪዎች "ይህንን ለማድረግ ትክክለኛው ጊዜ ሲመጣ ከሩሲያ ጋር በብቃት ለመወያየት ምን እንደሚያስፈልገን" እየተማከሩ እንደሆነ ጠቅሰዋል።
በአሜሪካ በተመራው የተኩስ አቁም ስምምነት መሠረት ኪዬቭ እና ሞስኮ አንድ ሺህ እስረኞችን ለመለዋወጥም ተስማምተዋል። ፑቲን ቅዳሜ ዕለት ሩሲያ ስለልውውጡ ምንም ዓይነት መረጃ ከዩክሬን በኩል እስካሁን እንዳልሰማች ተናግረዋል።
በሁለት አስርት ዓመታት ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ በ'ቀዩ አደባባይ' ሠልፍ ላይ ምንም ዓይነት ወታደራዊ መሳሪያ ያልታየ ሲሆን ክሪምሊን በተለምዶ የሩሲያን ወታደራዊ ኃይል ለዓለም አቀፍ መድረክ የምታሳይበት ሰልፍ ነው።
በዝግጅቱ ላይ የተሳተፉት ጋዜጠኞች በጣም ጥቂት የነበሩ ሲሆን ብዙ ዓለም አቀፍ የሚዲያ ተቋማት ፈቃድ አልተሰጣቸውም።
BBC
ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን አገራቸው ከዩክሬን ጋር እያካሄደች ያለችው ጦርነት እያበቃ ነው ብለው እንደሚያስቡ ተናገሩ።
ፕሬዚዳንቱ ይህንን ያሉት ሶቪየት ኅብረት ናዚ ጀርመንን ድል ያደረገችበትን በዓል ካከበረች በኋላ ከጋዜጠኞች ጋር በነበራቸው ቆይታ ወቅት ነው።
"ጉዳዩ እየተጠናቀቀ ነው ብዬ አስባለሁ" ሲሉ በዩክሬን እየተካሄደ ስለሚገኘው "ልዩ ወታደራዊ ዘመቻ" ተናግረው ምዕራባውያን ለኪዬቭ መንግሥትን የሚያደርጉትን ድጋፍ ኮንነዋል።
የሩሲያ ዓመታዊ የድል በዓል ዩክሬን በቀዩ አደባባይ በድሮኖች ጥቃት ልታደርስ ትችላለች በሚል ስጋት የተለመደውን የታንክ እና የሚሳኤል ሠልፍ አላካሄዱም።
የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በመጨረሻ ደቂቃ ባደራደሩት እና በሞስኮ እና በኪየቭ መካከል በተደረገ የተኩስ አቁም ስምምነት የጥቃት ስጋቱ ቀንሶ ሠልፉ ያለ ምንም አደጋ ተጠናቋል።
ፑቲን አስተያየትቱን የሰጡት የድል ቀን ንግግራቸውን ጦርነቱን ምክንያታዊነት ለማረጋገጥ ከተጠቀሙ ከጥቂት ሰዓታት በኋላ ነው።
በንግግራቸውም ሩሲያ "ፍትሃዊ" ጦርነት እየተዋጋች እንደሆነ እና ዩክሬንን "በኔቶ የሚታጠቀ እና የሚደገፍ ጠበኛ ኃይል" ብለው ጠርተዋታል።
ምዕራባውያን ዩክሬንን ስለመርዳታቸው በተመለከተ በጋዜጣዊ መግለጫ ወቅት የተጠየቁት ፑቲን "እርዳታ ቃል ገብተው እስከ ዛሬ ድረስም ከሩሲያ ጋር ግጭቱን ማቀጣጠል ጀመሩ። ጉዳዩ እያበቃ ነው ብዬ ባስብም ግን ከባድ ጉዳይ ነው" ሲሉ ምላሽ ሰጥተዋል።
የሩሲያ ኃይሎች በ2014 ክሬሚያን እና የምሥራቅ ዩክሬን ክፍሎችን የተቆጣጠሩ ሲሆን እአአ በየካቲት 2022 የዩክሬን ሙሉ ወረራን ጀመሩ።
ፑቲን የዩክሬን ፕሬዝዳንት ቮሎዲሚር ዜሌንስኪን የሚያገኙት ዘላቂ የሰላም ስምምነት ከተደረሰ በኋላ ብቻ እንደሆነ ተናግረዋል።
"በሦስተኛ አገር መገናኘትም ቢቻልም ግን በዚህ ዝግጅት ላይ ለመሳተፍ እና ለመፈረም የረዥም ጊዜ ታሪካዊ እይታን ለመፍጠር የሰላም ስምምነት ላይ የመጨረሻ ስምምነቶች ከተደረሱ በኋላ ብቻ ነው። ይህም የመጨረሻ እርምጃ መሆን አለበት" ሲሉ አክለዋል።
ዜሌንስኪ በግል ሊያገኟቸው ዝግጁ መሆናቸውን ቢሰሙም "እንዲህ አይነት መግለጫዎችን ስንሰማ ይህ የመጀመሪያ ጊዜ አይደለም" ብለዋል ፑቲን።
ፑቲን ለአውሮፓ አዲስ የደህንነት ስምምነቶችን ለመደራደር ፈቃደኛ እንደሆኑ እና የሚመርጡት የድርድር አጋር የጀርመን የቀድሞ ቻንስለር ጄርሃርድ ሽሮደር እንደሆኑ ጠቅሰዋል።
የቀድሞው ቻንስለር የፑቲን የረዠም ጊዜ ወዳጅ ሲሆኑ በሩሲያ መንግሥት ባለቤትነት ስር ላሉ የኤነርጂ ኩባንያዎች ላይ በመሥራታቸው ምክንያት አወዛጋቢ ናቸው።
ባለፈው ሳምንት የአውሮፓ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት አንቶኒዮ ኮስታ የአውሮፓ ኅብረት ከሩሲያ ጋር ለመደራደር "ተስፋ" እንዳለው እና ዜሌንስኪ እንዲህ ዓይነት እርምጃን እንደሚደግፉ እንደሚያምኑ ተናግረዋል።
በፋይናንሺያል ታይምስ በተጠቀሰው የኮስታ ንግግር መሠረት የአውሮፓ ኅብረት መሪዎች "ይህንን ለማድረግ ትክክለኛው ጊዜ ሲመጣ ከሩሲያ ጋር በብቃት ለመወያየት ምን እንደሚያስፈልገን" እየተማከሩ እንደሆነ ጠቅሰዋል።
በአሜሪካ በተመራው የተኩስ አቁም ስምምነት መሠረት ኪዬቭ እና ሞስኮ አንድ ሺህ እስረኞችን ለመለዋወጥም ተስማምተዋል። ፑቲን ቅዳሜ ዕለት ሩሲያ ስለልውውጡ ምንም ዓይነት መረጃ ከዩክሬን በኩል እስካሁን እንዳልሰማች ተናግረዋል።
በሁለት አስርት ዓመታት ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ በ'ቀዩ አደባባይ' ሠልፍ ላይ ምንም ዓይነት ወታደራዊ መሳሪያ ያልታየ ሲሆን ክሪምሊን በተለምዶ የሩሲያን ወታደራዊ ኃይል ለዓለም አቀፍ መድረክ የምታሳይበት ሰልፍ ነው።
በዝግጅቱ ላይ የተሳተፉት ጋዜጠኞች በጣም ጥቂት የነበሩ ሲሆን ብዙ ዓለም አቀፍ የሚዲያ ተቋማት ፈቃድ አልተሰጣቸውም።
BBC
3 months ago
ፕሬዝዳንት ትራምፕ አሜሪካ ላቀረበችው የድርድር ዕቅድ የኢራንን ምላሽ እየጠበቁ መሆኑን ተናገሩ
ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ጦርነቱን ለመቋጨት በቀረበው የአሜሪካ የስምምነት ዕቅድ ላይ የኢራንን ምላሽ ለማግኘት እየጠበቁ መሆኑን ለጋዜጠኞች ተናገሩ።
አሜሪካ ባለ 14 ነጥብ የስምምነት ዕቅድ አዘጋጅታ ወደ ኢራን መላኳ የተሰማው በዚህ ሳምንት ነበር። የመግባቢያ ስምምነት እንደሚሆን የተገለጸው ይህ ሰነድ ከያዛቸው ነጥቦች መካከል ኢራን ኒውክሌር የማበልጸግ ተግባሯን እንድታቆም ስለማድረግ የሚለው ይገኝበታል።
ኢራን ላይ የተጣሉ ማዕቀቦችን ማንሳት እና በሆርሙዝ ወሽመጥ በኩል የሚደረግ ነጻ ጉዞን መመለስም ተካትተዋል። በመጨረሻ ይደረሳል ተብሎ የሚጠበቀው የሰላም ስምምነት የሚመሠረተው በዚህ ዕቅድ ውስጥ በተካተቱት ነጥቦች ላይ እንደሚሆንም ተዘግቦ ነበር።
ኢራን ዕቅዱን እየገመገመች መሆኑን በውጭ ጉዳይ ሚኒስትሯ በኩል አስታውቃ ነበር። ይሁን እንጂ ሁለቱ አገራት ሐሙስ ምሽት አንዳቸው በሌላኛቸው ላይ ጥቃት ፈጽመዋል።
ትናንት አርብ ምሽት ኢራን ለዕቅዱ ምላሽ ሰጥታ እንደሆነ የተጠየቁት ትራምፕ፤ “ምናልባት ዛሬ ምሽት [ምላሻቸውን] እንሰማለን" ብለዋል።
ኢራን ሆን ብላ ድርድሩን እያጓተተች ነው ብለው ያምኑ እንደሆን የተጠየቁት ትራምፕ፤ "አላውቅም" የሚል ምላሽ መስጠታቸውን ሲኤንኤን ዘግቧል። "በቅርቡ እናውቃለን" ሲሉም አክለዋል።
ትራምፕ ይህንን ከማለታቸው ሰዓታትን አስቀድሞም የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ ኢራን ዛሬ ምላሽ ትሰጣለች ተብሎ እንደሚጠበቅ ተናግረው ነበር።
ሚኒስትሩ ጣሊያን ውስጥ ለጋዜጠኞች እንደተናገሩት "ምላሻቸውን ዛሬ የሆነ ሰዓት ላይ እንሰማለን ብለን እንጠብቃለን. . . ምላሻቸውም የምር እንደሚሆን ተስፋ አደርጋለሁ” ብለዋል።
እስካሁኑ ሰዓት ድረስ ግን ኢራን ምላሽ ስለመስጠቷ አልተረጋገጠም።
BBC
ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ጦርነቱን ለመቋጨት በቀረበው የአሜሪካ የስምምነት ዕቅድ ላይ የኢራንን ምላሽ ለማግኘት እየጠበቁ መሆኑን ለጋዜጠኞች ተናገሩ።
አሜሪካ ባለ 14 ነጥብ የስምምነት ዕቅድ አዘጋጅታ ወደ ኢራን መላኳ የተሰማው በዚህ ሳምንት ነበር። የመግባቢያ ስምምነት እንደሚሆን የተገለጸው ይህ ሰነድ ከያዛቸው ነጥቦች መካከል ኢራን ኒውክሌር የማበልጸግ ተግባሯን እንድታቆም ስለማድረግ የሚለው ይገኝበታል።
ኢራን ላይ የተጣሉ ማዕቀቦችን ማንሳት እና በሆርሙዝ ወሽመጥ በኩል የሚደረግ ነጻ ጉዞን መመለስም ተካትተዋል። በመጨረሻ ይደረሳል ተብሎ የሚጠበቀው የሰላም ስምምነት የሚመሠረተው በዚህ ዕቅድ ውስጥ በተካተቱት ነጥቦች ላይ እንደሚሆንም ተዘግቦ ነበር።
ኢራን ዕቅዱን እየገመገመች መሆኑን በውጭ ጉዳይ ሚኒስትሯ በኩል አስታውቃ ነበር። ይሁን እንጂ ሁለቱ አገራት ሐሙስ ምሽት አንዳቸው በሌላኛቸው ላይ ጥቃት ፈጽመዋል።
ትናንት አርብ ምሽት ኢራን ለዕቅዱ ምላሽ ሰጥታ እንደሆነ የተጠየቁት ትራምፕ፤ “ምናልባት ዛሬ ምሽት [ምላሻቸውን] እንሰማለን" ብለዋል።
ኢራን ሆን ብላ ድርድሩን እያጓተተች ነው ብለው ያምኑ እንደሆን የተጠየቁት ትራምፕ፤ "አላውቅም" የሚል ምላሽ መስጠታቸውን ሲኤንኤን ዘግቧል። "በቅርቡ እናውቃለን" ሲሉም አክለዋል።
ትራምፕ ይህንን ከማለታቸው ሰዓታትን አስቀድሞም የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ ኢራን ዛሬ ምላሽ ትሰጣለች ተብሎ እንደሚጠበቅ ተናግረው ነበር።
ሚኒስትሩ ጣሊያን ውስጥ ለጋዜጠኞች እንደተናገሩት "ምላሻቸውን ዛሬ የሆነ ሰዓት ላይ እንሰማለን ብለን እንጠብቃለን. . . ምላሻቸውም የምር እንደሚሆን ተስፋ አደርጋለሁ” ብለዋል።
እስካሁኑ ሰዓት ድረስ ግን ኢራን ምላሽ ስለመስጠቷ አልተረጋገጠም።
BBC
4 months ago
"ኢራንን በከባድ እርምጃ ወደ ድንጋይ ዘመን እንመልሳታለን" - ትራምፕ
የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ኢራንን እንደሚያወድሙ ዛቱ።
ፕሬዚዳንቱ "በሚቀጥሉት ሁለት ወይም ሶስት ሳምንታት ዩናይትድስቴትስ በኢራን ላይ ጥቃት ታደርሳለች" ብለዋል።
ትራምፕ በነጩ ቤተመንግሥት በሰጡት መግለጫ "ኢራንን በከባድ እርምጃ ወደ ድንጋይ ዘመን እንመልሳታለን" ሲሉ ዝተዋል።
"ዛሬ ላይ በቅርቡ ወታደራዊ ዓላማችንን ለማሳካት በትክክለኛው መንገድ ላይ ነን ብየ መናገር እችላለሁ" ሲሉ ተደምጠዋል።
"አላማችን ቀላል እና ግልጽ ነው" ያሉት ትራምፕ፣ "ኢራን በአካባቢው ሀያል እንዳትሆን ማድረግ ነው" በማለት ገልፀዋል።
ይሁን እንጂ ፕሬዚዳንቱ በትናንትናው እለት "ከተቻለ በሁለት ሳምንት፣ ምናልባት ደግሞ በሶስት ሳምንት ውስጥ ኢራንን ለቀን እንወጣለን" ሲሉ ተናግረው ነበር።
seledadotio
seledadotio
የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ኢራንን እንደሚያወድሙ ዛቱ።
ፕሬዚዳንቱ "በሚቀጥሉት ሁለት ወይም ሶስት ሳምንታት ዩናይትድስቴትስ በኢራን ላይ ጥቃት ታደርሳለች" ብለዋል።
ትራምፕ በነጩ ቤተመንግሥት በሰጡት መግለጫ "ኢራንን በከባድ እርምጃ ወደ ድንጋይ ዘመን እንመልሳታለን" ሲሉ ዝተዋል።
"ዛሬ ላይ በቅርቡ ወታደራዊ ዓላማችንን ለማሳካት በትክክለኛው መንገድ ላይ ነን ብየ መናገር እችላለሁ" ሲሉ ተደምጠዋል።
"አላማችን ቀላል እና ግልጽ ነው" ያሉት ትራምፕ፣ "ኢራን በአካባቢው ሀያል እንዳትሆን ማድረግ ነው" በማለት ገልፀዋል።
ይሁን እንጂ ፕሬዚዳንቱ በትናንትናው እለት "ከተቻለ በሁለት ሳምንት፣ ምናልባት ደግሞ በሶስት ሳምንት ውስጥ ኢራንን ለቀን እንወጣለን" ሲሉ ተናግረው ነበር።
seledadotio
seledadotio
Sponsored by
Surafel
4 months ago
''በቅርቡ የሚገቡ አሉ በስልክ ተወያይተናል'' ሜጄር ጄኔራል ተስፋዬ አያሌው''
የ13ኛ ዕዝ አዛዥ ሜጄር ጄኔራል ተስፋዬ አያሌው በጫካ የሚገኙ ታጣቂዎች በሰላም እንዲገቡ ተደጋጋሚ የሰላም ጥሪ ሲቀርብ መቆየቱን ተናግረው በቅርቡ የሚገቡ አሉ በስልክ ተወያይተናል ብለዋል።
በተደረገው የሰላም ጥሪ ፍቅሩ ሙሉዬ እና ጓደኞቹ የሰላም ጥሪውን መቀበላቸውን ገልፀው ''የፍቅሩ ተከታዮችም እንደሚመጡ ይጠበቃል ነው ያሉት።
ፍቅሩ እና ጓደኞቹ እንኳን በደህና መጣችሁ በማለት ፍቅሩ በሀገር መከላከያ ውስጥ እንደነበርም አስታውሰዋል።
የአማራ ሕዝብ ከዚህ በኋላ የጦርነት ቀጣና መሆን የለበትም ያሉት አዛዡ ሰላምን እንፍጠር በሚሉ ምክክሮች ተስማምቶ ሰላምን ፍልጎ በመምጣቱ እንኳን ደህና መጣህ ማለት እፈልጋለሁ ብለዋል።
seledadotio
seledadotio
የ13ኛ ዕዝ አዛዥ ሜጄር ጄኔራል ተስፋዬ አያሌው በጫካ የሚገኙ ታጣቂዎች በሰላም እንዲገቡ ተደጋጋሚ የሰላም ጥሪ ሲቀርብ መቆየቱን ተናግረው በቅርቡ የሚገቡ አሉ በስልክ ተወያይተናል ብለዋል።
በተደረገው የሰላም ጥሪ ፍቅሩ ሙሉዬ እና ጓደኞቹ የሰላም ጥሪውን መቀበላቸውን ገልፀው ''የፍቅሩ ተከታዮችም እንደሚመጡ ይጠበቃል ነው ያሉት።
ፍቅሩ እና ጓደኞቹ እንኳን በደህና መጣችሁ በማለት ፍቅሩ በሀገር መከላከያ ውስጥ እንደነበርም አስታውሰዋል።
የአማራ ሕዝብ ከዚህ በኋላ የጦርነት ቀጣና መሆን የለበትም ያሉት አዛዡ ሰላምን እንፍጠር በሚሉ ምክክሮች ተስማምቶ ሰላምን ፍልጎ በመምጣቱ እንኳን ደህና መጣህ ማለት እፈልጋለሁ ብለዋል።
seledadotio
seledadotio
5 months ago
አሜሪካ ለኢራን ባለ 15 ነጥብ የተኩስ አቁም የስምምነት ሃሳብ በፓኪስታን በኩል ማቅረቧ ተዘገበ።
አሜሪካ የተኩስ አቁም ሃሳቡን በፓኪስታን አምባሳደሮች በኩል ለኢራን ማቅረቧን የኢስላማባድ ባለስልጣናት ዛሬ አረጋግጠዋል። አሜሪካ የሰላም የስምምነት ሃሳብ ማቅረቧ የተሰማው ተጨማሪ የአየር ወለድ ወታደሮቿን ወደ መካከለኛው ምስራቅ ሃገራት እያሰማራች ባለችበት ወቅት ነው።
በፓኪስታን በኩል ለኢራን ቀረበ የተባለው የፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ "የሰላም ዕቅድ" 15 ነጥቦች ያካተተ ሲሆን አብዛኞቹ ሐሳቦች ኢራንን የሚያስገድዱ ናቸው ተብሏል።
ከእነዚህ መካከል በኢራን የሚሳይል ፕሮግራም ላይ ገደብ መጣል እና በሆርሙዝ ወሽመጥ በኩል መርከቦች በነፃነት እንዲንቀሳቀሱ መፍቀድ ፣ የዓለም አቀፉ የአቶሚክ ኢነርጂ ኤጀንሲ (IAEA) ጥብቅ ቁጥጥር ማድረግ ፣ የኢራንን የኑክሌር መርሃ ግብር መቀነስ ፣ በሲቪል የኑክሌር መስክ ላይ መተባበር እና በኢራን ላይ የተጣሉ ማዕቀቦችን ማንሳት እንደሚገኙበት ስማቸው እንዳይጠቀስ የጠየቁ የፓኪስታን ባለስጣናት ተናግረዋል።
አሜሪካ የተኩስ አቁም ሃሳብ አቀረበች ይባል እንጂ ተጨማሪ ወታደሮችን ወደ ቀጣናው ከመላክ ግን አላቀባትም። አሜሪካ በትንሹ 1,000 የሚሆኑ የ82ኛው የአየር ወለድ ክፍለ ጦር አባላት ወደ ቀጠናው እንደሚላኩ ተገልጿል። ይህም ቀደም ብለው ከተሰማሩት 5,000 የባህር ኃይል ወታደሮች በተጨማሪ ነው።
ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ ዩናይትድ ስቴትስ "ትክክለኛ ሰዎች" ካሏቸው ጋር የኢራን ጦርነትን ለማብቃት እየተነጋገረች እንደምትገኝ በዋይት ሐውስ ለጋዜጠኞች ተናግረው ነበር። ፕሬዝደንቱ ኢራን ሥምምነት ላይ የመድረስ ከፍተኛ ፍላጎት እንዳላት ገልጸዋል።
አንድ የኢራን ወታደራዊ ቃል አቀባይ ግን ዩናይትድ ስቴትስ ከራሷ ጋር እየተደራደረች እንደሆነ በመግለጽ የተባለውን ዲፕሎማሲያዊ ጥረት አጣጥለዋል።
ኢራን በእስራኤል እና በሌሎች የባህረ ሰላጤው ሃገራት ላይ የምትፈጽማቸውን ጥቃቶች አጠናክራ መቀጠሏን አሶሽየትድ ፕረስ ዘግቧል። በዚህም በኩዌት ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ላይ በደረሰ ጥቃት ከፍተኛ እሳት መነሳቱና ከፍተኛ ጭስ ሲወጣ መታየቱ ተነግሯል።
የእስራኤል መከላከያ ሠራዊት በሰሜን ምዕራብ ኢራን በሚገኘው ቃዝቪን ከተማ ላይ ሰፊ የአየር ድብደባ መጀመሩን አስታውቋል።
የኢራን ጤና ሚኒስቴር በአሜሪካ እና እስራኤል ጥምር ጥቃት የሟቾች ቁጥር ከ1,500 በላይ መድረሱን ገልጿል።
እስራኤል በተናጥል ባደረሰችው ጥቃት ሊባኖስ ውስጥ ከ1,000 በላይ ሰዎች ተገድለዋል።
ኢራን በበኩሏ ባደረሰችው የሚሳኤል እና የድሮን ጥቃት እስራኤል ውስጥ 16 ሰዎች መሞታቸው ተነግሯል። በተጨማሪም 13 የአሜሪካ ወታደራዊ አባላት ሕይወታቸውን አጥተዋል።
በጦርነቱ ለጊዜው በቁጥር ያልተገለጸ በሺዎች በሚቆጠሩ ሰዎች ላይ ጉዳት ደርሷል።
በጦርነቱ ምክንያት የጨመረው የነዳጅ ዋጋ አሁንም መቀነስ አላሳየም ። በአሁኑ ወቅት አንድ በርሜል ድፍድፍ ነዳጅ በ100 ዶላር አካባቢ እየተሸጠ ይገኛል። ይህም ጦርነቱ ከመጀመሩ በፊት ከነበረው ዋጋ የ40 በመቶ ጭማሪ አለው።
DW Amharic
አሜሪካ የተኩስ አቁም ሃሳቡን በፓኪስታን አምባሳደሮች በኩል ለኢራን ማቅረቧን የኢስላማባድ ባለስልጣናት ዛሬ አረጋግጠዋል። አሜሪካ የሰላም የስምምነት ሃሳብ ማቅረቧ የተሰማው ተጨማሪ የአየር ወለድ ወታደሮቿን ወደ መካከለኛው ምስራቅ ሃገራት እያሰማራች ባለችበት ወቅት ነው።
በፓኪስታን በኩል ለኢራን ቀረበ የተባለው የፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ "የሰላም ዕቅድ" 15 ነጥቦች ያካተተ ሲሆን አብዛኞቹ ሐሳቦች ኢራንን የሚያስገድዱ ናቸው ተብሏል።
ከእነዚህ መካከል በኢራን የሚሳይል ፕሮግራም ላይ ገደብ መጣል እና በሆርሙዝ ወሽመጥ በኩል መርከቦች በነፃነት እንዲንቀሳቀሱ መፍቀድ ፣ የዓለም አቀፉ የአቶሚክ ኢነርጂ ኤጀንሲ (IAEA) ጥብቅ ቁጥጥር ማድረግ ፣ የኢራንን የኑክሌር መርሃ ግብር መቀነስ ፣ በሲቪል የኑክሌር መስክ ላይ መተባበር እና በኢራን ላይ የተጣሉ ማዕቀቦችን ማንሳት እንደሚገኙበት ስማቸው እንዳይጠቀስ የጠየቁ የፓኪስታን ባለስጣናት ተናግረዋል።
አሜሪካ የተኩስ አቁም ሃሳብ አቀረበች ይባል እንጂ ተጨማሪ ወታደሮችን ወደ ቀጣናው ከመላክ ግን አላቀባትም። አሜሪካ በትንሹ 1,000 የሚሆኑ የ82ኛው የአየር ወለድ ክፍለ ጦር አባላት ወደ ቀጠናው እንደሚላኩ ተገልጿል። ይህም ቀደም ብለው ከተሰማሩት 5,000 የባህር ኃይል ወታደሮች በተጨማሪ ነው።
ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ ዩናይትድ ስቴትስ "ትክክለኛ ሰዎች" ካሏቸው ጋር የኢራን ጦርነትን ለማብቃት እየተነጋገረች እንደምትገኝ በዋይት ሐውስ ለጋዜጠኞች ተናግረው ነበር። ፕሬዝደንቱ ኢራን ሥምምነት ላይ የመድረስ ከፍተኛ ፍላጎት እንዳላት ገልጸዋል።
አንድ የኢራን ወታደራዊ ቃል አቀባይ ግን ዩናይትድ ስቴትስ ከራሷ ጋር እየተደራደረች እንደሆነ በመግለጽ የተባለውን ዲፕሎማሲያዊ ጥረት አጣጥለዋል።
ኢራን በእስራኤል እና በሌሎች የባህረ ሰላጤው ሃገራት ላይ የምትፈጽማቸውን ጥቃቶች አጠናክራ መቀጠሏን አሶሽየትድ ፕረስ ዘግቧል። በዚህም በኩዌት ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ላይ በደረሰ ጥቃት ከፍተኛ እሳት መነሳቱና ከፍተኛ ጭስ ሲወጣ መታየቱ ተነግሯል።
የእስራኤል መከላከያ ሠራዊት በሰሜን ምዕራብ ኢራን በሚገኘው ቃዝቪን ከተማ ላይ ሰፊ የአየር ድብደባ መጀመሩን አስታውቋል።
የኢራን ጤና ሚኒስቴር በአሜሪካ እና እስራኤል ጥምር ጥቃት የሟቾች ቁጥር ከ1,500 በላይ መድረሱን ገልጿል።
እስራኤል በተናጥል ባደረሰችው ጥቃት ሊባኖስ ውስጥ ከ1,000 በላይ ሰዎች ተገድለዋል።
ኢራን በበኩሏ ባደረሰችው የሚሳኤል እና የድሮን ጥቃት እስራኤል ውስጥ 16 ሰዎች መሞታቸው ተነግሯል። በተጨማሪም 13 የአሜሪካ ወታደራዊ አባላት ሕይወታቸውን አጥተዋል።
በጦርነቱ ለጊዜው በቁጥር ያልተገለጸ በሺዎች በሚቆጠሩ ሰዎች ላይ ጉዳት ደርሷል።
በጦርነቱ ምክንያት የጨመረው የነዳጅ ዋጋ አሁንም መቀነስ አላሳየም ። በአሁኑ ወቅት አንድ በርሜል ድፍድፍ ነዳጅ በ100 ዶላር አካባቢ እየተሸጠ ይገኛል። ይህም ጦርነቱ ከመጀመሩ በፊት ከነበረው ዋጋ የ40 በመቶ ጭማሪ አለው።
DW Amharic
5 months ago
ራይድ ትራንስፖርት አገልግሎት ከቦሰተን ፓርትነርስ ጋር የስራ ስምምነት ተፈራረመ
መጋቢት 11፣ 2018 ዓ.ም
አዲሰ አበባ፣ኢትዮጵያ
ራይድ ትራንስፖርት ከቦስተን ፓረተነርስ ጋር ዓለም አቀፍ ይዘቱን የጠበቀ አገልግሎት ለመስጠት በሚችልበት ሁኔታ በጋራ ለመስራት የስራ ስምምነት ተፈራርሟል፡፡ ሁለቱ ተቋማት ግዙፍ አገልገሎት አቅራቢዎች እንደመሆናቸው መጠን በትብብር ለመስራት ተስማምተዋል፡፡
በፊርማ ስነ-ስርዓቱ ላይ የተገኙት የራይድ ትራንስፖርት ዋና ስራ አስፈፃሚ ወ/ሮ ሳምራዊት ፍቅሩ ራይድ ትራስፖርት በአገራችን የዲጂታል ትራንስፖርት አገልግሎት ፈር - ቀዳጅ እንደሆነ ገልፀው፣ ሰዎችን ከዕድሎች ጋር በማገኛኘት የዕለት ተዕለት የኑሮ ዘይቤያቸው የተሻለ እንዲሆን መስራት የተመሰረተበት ራዕይ መሆኑ አስረድተዋል ፡፡ ሰለሆነም ይህንን ራዕይ ለማሳካት ከተለያ አገር-አቀፍ እና ዓለምአቀፍ ድርጅቶች ጋር በትብብር እየሰራ እንደሚገኝ ገልፀው ከቦስተን ፓርትነርስ ጋር እያደረግን ያለነው ይህንኑ ዓላማችንን የበለጠ ለማሳለጥ ነው ብለዋል፡፡
በሌላ በኩል የቦስተን ፓረተነርስ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ታዲዎስ ጌታቸው ድርጅታቸው ላለፉት 24 ዓመታት አዳዲስ የቱሪዝም አገልግሎቶችን ለህብረተሰቡ ሲያቀርብ የቆየ ተቋም መሆኑን ተናግረው በተለያዩ ከተሞች አገልግሎቶቹን እያሰፋ ይገኛል ብለዋል፡፡ ከራይድ ጋር በምናደርገው ስምምነትም፡-
1ኛ እንደ እንጦጦ ፓርክ፣ አፍሪካ ቪሌጅ ፣ ኩሪፍቱ ቢሾፍቱ ሪዞርቶች ራይድ የኤሌክትሪክ መኪኖችን በመመደብ ከቦስተን ፓረተነርስ ጋር በጋራ ይሰራል፣
2ኛ በኩሪፍቱ ሪዞርቶች በሚካሄዱ ትልልቅ ስብሰባዎች፣የጋብቻ ስነ-ስርዓቶች እና ኮንሰርቶች በሚዘጋጁበት ወቅት ራይድ ትራንስፖርት በቂ እና አስተማማኝ ትራንስፖርት ያቀርባል
3ኛ የራይድ ትራንስፖርትንም ሆነ የቦስተን ፓርትነርስን አገልግሎቶችን መልካም ስም እና ዝና በጠበቀ መልኩ የጋራ የገበያ ትስስር፣ የማስተዋወቅ እና የብራንድ ፕሮሞሽን ስራዎችን በትብብር ይሰራሉ፡፡
4ኛ ራይድ ትራንስፖርት አግልግሎት ለኩርፍቱ ሪዞርት ÷ ለቦስተን ስፓ ደንበኞች ያለምንም እንግልት በሚንቀሳቅሱበት የቱሪስት መስህብ ዘመናዊ ትራንስፖርት ያቀርባል
5ኛ አዳዲስ የገበያ ተደራሽነትን የሚያሰፉ ፓኬጆችን በጋራ በማዘጋጀት ለተጠቃዎች ለማድረስ በጋራ እንስራለን ሲሉ በስምምነቱ ላይ ተናግረዋል፡፡
#fastmereja
መጋቢት 11፣ 2018 ዓ.ም
አዲሰ አበባ፣ኢትዮጵያ
ራይድ ትራንስፖርት ከቦስተን ፓረተነርስ ጋር ዓለም አቀፍ ይዘቱን የጠበቀ አገልግሎት ለመስጠት በሚችልበት ሁኔታ በጋራ ለመስራት የስራ ስምምነት ተፈራርሟል፡፡ ሁለቱ ተቋማት ግዙፍ አገልገሎት አቅራቢዎች እንደመሆናቸው መጠን በትብብር ለመስራት ተስማምተዋል፡፡
በፊርማ ስነ-ስርዓቱ ላይ የተገኙት የራይድ ትራንስፖርት ዋና ስራ አስፈፃሚ ወ/ሮ ሳምራዊት ፍቅሩ ራይድ ትራስፖርት በአገራችን የዲጂታል ትራንስፖርት አገልግሎት ፈር - ቀዳጅ እንደሆነ ገልፀው፣ ሰዎችን ከዕድሎች ጋር በማገኛኘት የዕለት ተዕለት የኑሮ ዘይቤያቸው የተሻለ እንዲሆን መስራት የተመሰረተበት ራዕይ መሆኑ አስረድተዋል ፡፡ ሰለሆነም ይህንን ራዕይ ለማሳካት ከተለያ አገር-አቀፍ እና ዓለምአቀፍ ድርጅቶች ጋር በትብብር እየሰራ እንደሚገኝ ገልፀው ከቦስተን ፓርትነርስ ጋር እያደረግን ያለነው ይህንኑ ዓላማችንን የበለጠ ለማሳለጥ ነው ብለዋል፡፡
በሌላ በኩል የቦስተን ፓረተነርስ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ታዲዎስ ጌታቸው ድርጅታቸው ላለፉት 24 ዓመታት አዳዲስ የቱሪዝም አገልግሎቶችን ለህብረተሰቡ ሲያቀርብ የቆየ ተቋም መሆኑን ተናግረው በተለያዩ ከተሞች አገልግሎቶቹን እያሰፋ ይገኛል ብለዋል፡፡ ከራይድ ጋር በምናደርገው ስምምነትም፡-
1ኛ እንደ እንጦጦ ፓርክ፣ አፍሪካ ቪሌጅ ፣ ኩሪፍቱ ቢሾፍቱ ሪዞርቶች ራይድ የኤሌክትሪክ መኪኖችን በመመደብ ከቦስተን ፓረተነርስ ጋር በጋራ ይሰራል፣
2ኛ በኩሪፍቱ ሪዞርቶች በሚካሄዱ ትልልቅ ስብሰባዎች፣የጋብቻ ስነ-ስርዓቶች እና ኮንሰርቶች በሚዘጋጁበት ወቅት ራይድ ትራንስፖርት በቂ እና አስተማማኝ ትራንስፖርት ያቀርባል
3ኛ የራይድ ትራንስፖርትንም ሆነ የቦስተን ፓርትነርስን አገልግሎቶችን መልካም ስም እና ዝና በጠበቀ መልኩ የጋራ የገበያ ትስስር፣ የማስተዋወቅ እና የብራንድ ፕሮሞሽን ስራዎችን በትብብር ይሰራሉ፡፡
4ኛ ራይድ ትራንስፖርት አግልግሎት ለኩርፍቱ ሪዞርት ÷ ለቦስተን ስፓ ደንበኞች ያለምንም እንግልት በሚንቀሳቅሱበት የቱሪስት መስህብ ዘመናዊ ትራንስፖርት ያቀርባል
5ኛ አዳዲስ የገበያ ተደራሽነትን የሚያሰፉ ፓኬጆችን በጋራ በማዘጋጀት ለተጠቃዎች ለማድረስ በጋራ እንስራለን ሲሉ በስምምነቱ ላይ ተናግረዋል፡፡
#fastmereja
5 months ago
ራይድ ትራንስፖርት አገልግሎት ከቦሰተን ፓርትነርስ ጋር የስራ ስምምነት ተፈራረመ
መጋቢት 11፣ 2018 ዓ.ም
አዲሰ አበባ፣ኢትዮጵያ
ራይድ ትራንስፖርት ከቦስተን ፓረተነርስ ጋር ዓለም አቀፍ ይዘቱን የጠበቀ አገልግሎት ለመስጠት በሚችልበት ሁኔታ በጋራ ለመስራት የስራ ስምምነት ተፈራርሟል፡፡ ሁለቱ ተቋማት ግዙፍ አገልገሎት አቅራቢዎች እንደመሆናቸው መጠን በትብብር ለመስራት ተስማምተዋል፡፡ በፊርማ ስነ-ስርዓቱ ላይ የተገኙት የራይድ ትራንስፖርት ዋና ስራ አስፈፃሚ ወ/ሮ ሳምራዊት ፍቅሩ ራይድ ትራስፖርት በአገራችን የዲጂታል ትራንስፖርት አገልግሎት ፈር - ቀዳጅ እንደሆነ ገልፀው፣ ሰዎችን ከዕድሎች ጋር በማገኛኘት የዕለት ተዕለት የኑሮ ዘይቤያቸው የተሻለ እንዲሆን መስራት የተመሰረተበት ራዕይ መሆኑ አስረድተዋል ፡፡ ሰለሆነም ይህንን ራዕይ ለማሳካት ከተለያ አገር-አቀፍ እና ዓለምአቀፍ ድርጅቶች ጋር በትብብር እየሰራ እንደሚገኝ ገልፀው ከቦስተን ፓርትነርስ ጋር እያደረግን ያለነው ይህንኑ ዓላማችንን የበለጠ ለማሳለጥ ነው ብለዋል፡፡
በሌላ በኩል የቦስተን ፓረተነርስ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ታዲዎስ ጌታቸው ድርጅታቸው ላለፉት 24 ዓመታት አዳዲስ የቱሪዝም አገልግሎቶችን ለህብረተሰቡ ሲያቀርብ የቆየ ተቋም መሆኑን ተናግረው በተለያዩ ከተሞች አገልግሎቶቹን እያሰፋ ይገኛል ብለዋል፡፡ ከራይድ ጋር በምናደርገው ስምምነትም፡-
1ኛ እንደ እንጦጦ ፓርክ፣ አፍሪካ ቪሌጅ ፣ ኩሪፍቱ ቢሾፍቱ ሪዞርቶች ራይድ የኤሌክትሪክ መኪኖችን በመመደብ ከቦስተን ፓረተነርስ ጋር በጋራ ይሰራል፣
2ኛ በኩሪፍቱ ሪዞርቶች በሚካሄዱ ትልልቅ ስብሰባዎች፣የጋብቻ ስነ-ስርዓቶች እና ኮንሰርቶች በሚዘጋጁበት ወቅት ራይድ ትራንስፖርት በቂ እና አስተማማኝ ትራንስፖርት ያቀርባል
3ኛ የራይድ ትራንስፖርትንም ሆነ የቦስተን ፓርትነርስን አገልግሎቶችን መልካም ስም እና ዝና በጠበቀ መልኩ የጋራ የገበያ ትስስር፣ የማስተዋወቅ እና የብራንድ ፕሮሞሽን ስራዎችን በትብብር ይሰራሉ፡፡
4ኛ ራይድ ትራንስፖርት አግልግሎት ለኩርፍቱ ሪዞርት ÷ ለቦስተን ስፓ ደንበኞች ያለምንም እንግልት በሚንቀሳቅሱበት የቱሪስት መስህብ ዘመናዊ ትራንስፖርት ያቀርባል
5ኛ አዳዲስ የገበያ ተደራሽነትን የሚያሰፉ ፓኬጆችን በጋራ በማዘጋጀት ለተጠቃዎች ለማድረስ በጋራ እንስራለን ሲሉ በስምምነቱ ላይ ተናግረዋል፡፡
መጋቢት 11፣ 2018 ዓ.ም
አዲሰ አበባ፣ኢትዮጵያ
ራይድ ትራንስፖርት ከቦስተን ፓረተነርስ ጋር ዓለም አቀፍ ይዘቱን የጠበቀ አገልግሎት ለመስጠት በሚችልበት ሁኔታ በጋራ ለመስራት የስራ ስምምነት ተፈራርሟል፡፡ ሁለቱ ተቋማት ግዙፍ አገልገሎት አቅራቢዎች እንደመሆናቸው መጠን በትብብር ለመስራት ተስማምተዋል፡፡ በፊርማ ስነ-ስርዓቱ ላይ የተገኙት የራይድ ትራንስፖርት ዋና ስራ አስፈፃሚ ወ/ሮ ሳምራዊት ፍቅሩ ራይድ ትራስፖርት በአገራችን የዲጂታል ትራንስፖርት አገልግሎት ፈር - ቀዳጅ እንደሆነ ገልፀው፣ ሰዎችን ከዕድሎች ጋር በማገኛኘት የዕለት ተዕለት የኑሮ ዘይቤያቸው የተሻለ እንዲሆን መስራት የተመሰረተበት ራዕይ መሆኑ አስረድተዋል ፡፡ ሰለሆነም ይህንን ራዕይ ለማሳካት ከተለያ አገር-አቀፍ እና ዓለምአቀፍ ድርጅቶች ጋር በትብብር እየሰራ እንደሚገኝ ገልፀው ከቦስተን ፓርትነርስ ጋር እያደረግን ያለነው ይህንኑ ዓላማችንን የበለጠ ለማሳለጥ ነው ብለዋል፡፡
በሌላ በኩል የቦስተን ፓረተነርስ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ታዲዎስ ጌታቸው ድርጅታቸው ላለፉት 24 ዓመታት አዳዲስ የቱሪዝም አገልግሎቶችን ለህብረተሰቡ ሲያቀርብ የቆየ ተቋም መሆኑን ተናግረው በተለያዩ ከተሞች አገልግሎቶቹን እያሰፋ ይገኛል ብለዋል፡፡ ከራይድ ጋር በምናደርገው ስምምነትም፡-
1ኛ እንደ እንጦጦ ፓርክ፣ አፍሪካ ቪሌጅ ፣ ኩሪፍቱ ቢሾፍቱ ሪዞርቶች ራይድ የኤሌክትሪክ መኪኖችን በመመደብ ከቦስተን ፓረተነርስ ጋር በጋራ ይሰራል፣
2ኛ በኩሪፍቱ ሪዞርቶች በሚካሄዱ ትልልቅ ስብሰባዎች፣የጋብቻ ስነ-ስርዓቶች እና ኮንሰርቶች በሚዘጋጁበት ወቅት ራይድ ትራንስፖርት በቂ እና አስተማማኝ ትራንስፖርት ያቀርባል
3ኛ የራይድ ትራንስፖርትንም ሆነ የቦስተን ፓርትነርስን አገልግሎቶችን መልካም ስም እና ዝና በጠበቀ መልኩ የጋራ የገበያ ትስስር፣ የማስተዋወቅ እና የብራንድ ፕሮሞሽን ስራዎችን በትብብር ይሰራሉ፡፡
4ኛ ራይድ ትራንስፖርት አግልግሎት ለኩርፍቱ ሪዞርት ÷ ለቦስተን ስፓ ደንበኞች ያለምንም እንግልት በሚንቀሳቅሱበት የቱሪስት መስህብ ዘመናዊ ትራንስፖርት ያቀርባል
5ኛ አዳዲስ የገበያ ተደራሽነትን የሚያሰፉ ፓኬጆችን በጋራ በማዘጋጀት ለተጠቃዎች ለማድረስ በጋራ እንስራለን ሲሉ በስምምነቱ ላይ ተናግረዋል፡፡
Sponsored by
Surafel
5 months ago
ኢትዮጵያ የተቀቀለ ስጋን ወደ ቻይና ለመላክ የሚያስችላትን ደረጃ ማዘጋጀቷ ተገለፀ
ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት የስጋ ምርት ተቀባይ ሀገራትን ቁጥር ለመጨመር እና ከዘርፋ ያላትን ተጠቃሚነት ለማሳደግ አቅዳ እየሰራች ትገኛለች ሲል የግብርና ሚኒስቴር አስታውቋል። በሚኒስቴሩ የእንስሳት ምርት ሬጉላቶሪ መሪ ሥራ አስፈጻሚ ዶክተር አያሌው ሹመት ለብስራት ሬድዮ እንደገለፁት ኢትዮጵያ ካላት የእንስሳት ቁጥር አንፃር ምርትን ለውጪ ገበያ የመላክ ፍላጎት አላት።
አሁን ላይ የሀገራትን የምርት ጥራትና ደህንነት መስፈርትን በማሟላቷ የስጋ ምርቷን ኤክስፓርት ለማድረግ አቅዳ እየሰራች እንደምትገኝ ተናግረው ቻይና ከእነዚህ ሀገራት መካከል ተጠቃሽ ናት ብለዋል።በአብዛኛዉ የስጋ ምርቷን ጥቂተ በሆኑ የገልፍ ሀገራት ላይ ለሽያጭ የምታቀርበው ኢትዮጵያ የተቀቀለ የበግና የፍየል ስጋን ወደዚህች ለመላክ መዘጋጀቷ ተገልጿል።
ይህን እውን ለማድረግ ቻይና ስታነሳው ለነበረው የህግ ክፍተት ምላሽ መስጠት የሚያስችል ስራ መሰራቱ ተጠቅሷል።ኢትዮጵያ የቆየ ህግን ስትከተል በመቆየቷ የቻይናን የጥራትና ደህንነት መስፈርት በጠበቀ መልኩ ምርትን መላክ እንዲቻል ጥረት ሲደረግ መቆየቱን ያስረዱት ዶክተር አያሌው አሁን ላይ ለዚህ የሚረዳ ስታንዳርድ መዘጋጀቱን ተናግረዋል።
በአሁኑ ወቅት ኢትዮጵያ ይህን ምርት ወደ ቻይና ለመላክ ከምትችልበት የመጨረሻው ደረጃ ላይ መድረሷን ጠቁመው በዚህ አመት መጨረሻ ላይ የመግባቢያ ሰነድ ስምምነት እንደምትፈራረም ዶክተር አያሌው ጨምረው ለጣቢያችን ገልፀዋል።
seledadotio
seledadotio
ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት የስጋ ምርት ተቀባይ ሀገራትን ቁጥር ለመጨመር እና ከዘርፋ ያላትን ተጠቃሚነት ለማሳደግ አቅዳ እየሰራች ትገኛለች ሲል የግብርና ሚኒስቴር አስታውቋል። በሚኒስቴሩ የእንስሳት ምርት ሬጉላቶሪ መሪ ሥራ አስፈጻሚ ዶክተር አያሌው ሹመት ለብስራት ሬድዮ እንደገለፁት ኢትዮጵያ ካላት የእንስሳት ቁጥር አንፃር ምርትን ለውጪ ገበያ የመላክ ፍላጎት አላት።
አሁን ላይ የሀገራትን የምርት ጥራትና ደህንነት መስፈርትን በማሟላቷ የስጋ ምርቷን ኤክስፓርት ለማድረግ አቅዳ እየሰራች እንደምትገኝ ተናግረው ቻይና ከእነዚህ ሀገራት መካከል ተጠቃሽ ናት ብለዋል።በአብዛኛዉ የስጋ ምርቷን ጥቂተ በሆኑ የገልፍ ሀገራት ላይ ለሽያጭ የምታቀርበው ኢትዮጵያ የተቀቀለ የበግና የፍየል ስጋን ወደዚህች ለመላክ መዘጋጀቷ ተገልጿል።
ይህን እውን ለማድረግ ቻይና ስታነሳው ለነበረው የህግ ክፍተት ምላሽ መስጠት የሚያስችል ስራ መሰራቱ ተጠቅሷል።ኢትዮጵያ የቆየ ህግን ስትከተል በመቆየቷ የቻይናን የጥራትና ደህንነት መስፈርት በጠበቀ መልኩ ምርትን መላክ እንዲቻል ጥረት ሲደረግ መቆየቱን ያስረዱት ዶክተር አያሌው አሁን ላይ ለዚህ የሚረዳ ስታንዳርድ መዘጋጀቱን ተናግረዋል።
በአሁኑ ወቅት ኢትዮጵያ ይህን ምርት ወደ ቻይና ለመላክ ከምትችልበት የመጨረሻው ደረጃ ላይ መድረሷን ጠቁመው በዚህ አመት መጨረሻ ላይ የመግባቢያ ሰነድ ስምምነት እንደምትፈራረም ዶክተር አያሌው ጨምረው ለጣቢያችን ገልፀዋል።
seledadotio
seledadotio
5 months ago
ኢትዮጵያ የተቀቀለ ስጋን ወደ ቻይና ለመላክ የሚያስችላትን ደረጃ ማዘጋጀቷ ተገለፀ
ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት የስጋ ምርት ተቀባይ ሀገራትን ቁጥር ለመጨመር እና ከዘርፋ ያላትን ተጠቃሚነት ለማሳደግ አቅዳ እየሰራች ትገኛለች ሲል የግብርና ሚኒስቴር አስታውቋል። በሚኒስቴሩ የእንስሳት ምርት ሬጉላቶሪ መሪ ሥራ አስፈጻሚ ዶክተር አያሌው ሹመት ለብስራት ሬድዮ እንደገለፁት ኢትዮጵያ ካላት የእንስሳት ቁጥር አንፃር ምርትን ለውጪ ገበያ የመላክ ፍላጎት አላት።
አሁን ላይ የሀገራትን የምርት ጥራትና ደህንነት መስፈርትን በማሟላቷ የስጋ ምርቷን ኤክስፓርት ለማድረግ አቅዳ እየሰራች እንደምትገኝ ተናግረው ቻይና ከእነዚህ ሀገራት መካከል ተጠቃሽ ናት ብለዋል።በአብዛኛዉ የስጋ ምርቷን ጥቂተ በሆኑ የገልፍ ሀገራት ላይ ለሽያጭ የምታቀርበው ኢትዮጵያ የተቀቀለ የበግና የፍየል ስጋን ወደዚህች ለመላክ መዘጋጀቷ ተገልጿል።
ይህን እውን ለማድረግ ቻይና ስታነሳው ለነበረው የህግ ክፍተት ምላሽ መስጠት የሚያስችል ስራ መሰራቱ ተጠቅሷል።ኢትዮጵያ የቆየ ህግን ስትከተል በመቆየቷ የቻይናን የጥራትና ደህንነት መስፈርት በጠበቀ መልኩ ምርትን መላክ እንዲቻል ጥረት ሲደረግ መቆየቱን ያስረዱት ዶክተር አያሌው አሁን ላይ ለዚህ የሚረዳ ስታንዳርድ መዘጋጀቱን ተናግረዋል።
በአሁኑ ወቅት ኢትዮጵያ ይህን ምርት ወደ ቻይና ለመላክ ከምትችልበት የመጨረሻው ደረጃ ላይ መድረሷን ጠቁመው በዚህ አመት መጨረሻ ላይ የመግባቢያ ሰነድ ስምምነት እንደምትፈራረም ዶክተር አያሌው ጨምረው ለጣቢያችን ገልፀዋል።
በቅድስት ደጀኔ
#ዳጉ_ጆርናል
ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት የስጋ ምርት ተቀባይ ሀገራትን ቁጥር ለመጨመር እና ከዘርፋ ያላትን ተጠቃሚነት ለማሳደግ አቅዳ እየሰራች ትገኛለች ሲል የግብርና ሚኒስቴር አስታውቋል። በሚኒስቴሩ የእንስሳት ምርት ሬጉላቶሪ መሪ ሥራ አስፈጻሚ ዶክተር አያሌው ሹመት ለብስራት ሬድዮ እንደገለፁት ኢትዮጵያ ካላት የእንስሳት ቁጥር አንፃር ምርትን ለውጪ ገበያ የመላክ ፍላጎት አላት።
አሁን ላይ የሀገራትን የምርት ጥራትና ደህንነት መስፈርትን በማሟላቷ የስጋ ምርቷን ኤክስፓርት ለማድረግ አቅዳ እየሰራች እንደምትገኝ ተናግረው ቻይና ከእነዚህ ሀገራት መካከል ተጠቃሽ ናት ብለዋል።በአብዛኛዉ የስጋ ምርቷን ጥቂተ በሆኑ የገልፍ ሀገራት ላይ ለሽያጭ የምታቀርበው ኢትዮጵያ የተቀቀለ የበግና የፍየል ስጋን ወደዚህች ለመላክ መዘጋጀቷ ተገልጿል።
ይህን እውን ለማድረግ ቻይና ስታነሳው ለነበረው የህግ ክፍተት ምላሽ መስጠት የሚያስችል ስራ መሰራቱ ተጠቅሷል።ኢትዮጵያ የቆየ ህግን ስትከተል በመቆየቷ የቻይናን የጥራትና ደህንነት መስፈርት በጠበቀ መልኩ ምርትን መላክ እንዲቻል ጥረት ሲደረግ መቆየቱን ያስረዱት ዶክተር አያሌው አሁን ላይ ለዚህ የሚረዳ ስታንዳርድ መዘጋጀቱን ተናግረዋል።
በአሁኑ ወቅት ኢትዮጵያ ይህን ምርት ወደ ቻይና ለመላክ ከምትችልበት የመጨረሻው ደረጃ ላይ መድረሷን ጠቁመው በዚህ አመት መጨረሻ ላይ የመግባቢያ ሰነድ ስምምነት እንደምትፈራረም ዶክተር አያሌው ጨምረው ለጣቢያችን ገልፀዋል።
በቅድስት ደጀኔ
#ዳጉ_ጆርናል
5 months ago
አምስት የአሜሪካ አውሮፕላኖች ሳዑዲ ውስጥ በኢራን ሚሳዔል ተመቱ
አምስት የአሜሪካ አየር ላይ ነዳጅ የሚሞሉ ወታደራዊ አውሮፕላኖች ሳዑዲ አረቢያ ውስጥ በኢራን ተመትተው ጉዳት እንደ ደረሰባቸው ዎል ስትሪት ጆርናል ዘገበ።
አውሮፕላኖቹ በሳዑዲው ልዑል ሱልጣን የአየር ኃይል ሰፈር ውስጥ ሳሉ ከቀናት በፊት ኢራን በፈጸመችው የሚሳዔል ጥቃት መመታታቸውን ጋዜጣው የአሜሪካ ባለሥልጣናትን ጠቅሶ ዘግቧል።
ነዳጅ ጫኝ የሆኑት ወታደራዊ አውሮፕላኖች በደረሰባቸው ጥቃት ጉዳት እንደረሰባቸው ነገር ግን ሙሉ ለሙሉ አለመውደማቸውን ባሥልጣናት ተናግረው “በአሁኑ ጊዜ ጥገና እየተደረገላቸው” መሆኑን እና በጥቃቱ በሰው ላይ ጉዳት አለመድረሱን መናገራቸውን ዎል ስትሪት ጆርናል ገልጿል።
ይህ በአምስት የአሜሪካ ወታደራዊ አውሮፕላን ላይ ጥቃት መፈጸሙን የሚገልጸው ዘገባ የወጣው ኬሲ-135 ነዳጅ የሚሞላ የአሜሪካ አየር ኃይል አውሮፕላን ባለፈው ሐሙስ በምዕራባዊ ኢራቅ ውስጥ መከስከሱ ከተነገረ በኋላ ነው።
በመካከለኛው ምሥራቅ የአሜሪካንን ወታደራዊ ተልዕኮዎች የሚቆጣጠረው የዩናይትድ ስቴትስ ጦር ኃይል ማዕከላዊ ዕዝ (ሴንትኮም) እንዳረጋገጠው በአደጋው በአውሮፕላኑ ውስጥ የነበሩ ሁሉም ስድስት አባላቱ ሞተዋል።
BBC
አምስት የአሜሪካ አየር ላይ ነዳጅ የሚሞሉ ወታደራዊ አውሮፕላኖች ሳዑዲ አረቢያ ውስጥ በኢራን ተመትተው ጉዳት እንደ ደረሰባቸው ዎል ስትሪት ጆርናል ዘገበ።
አውሮፕላኖቹ በሳዑዲው ልዑል ሱልጣን የአየር ኃይል ሰፈር ውስጥ ሳሉ ከቀናት በፊት ኢራን በፈጸመችው የሚሳዔል ጥቃት መመታታቸውን ጋዜጣው የአሜሪካ ባለሥልጣናትን ጠቅሶ ዘግቧል።
ነዳጅ ጫኝ የሆኑት ወታደራዊ አውሮፕላኖች በደረሰባቸው ጥቃት ጉዳት እንደረሰባቸው ነገር ግን ሙሉ ለሙሉ አለመውደማቸውን ባሥልጣናት ተናግረው “በአሁኑ ጊዜ ጥገና እየተደረገላቸው” መሆኑን እና በጥቃቱ በሰው ላይ ጉዳት አለመድረሱን መናገራቸውን ዎል ስትሪት ጆርናል ገልጿል።
ይህ በአምስት የአሜሪካ ወታደራዊ አውሮፕላን ላይ ጥቃት መፈጸሙን የሚገልጸው ዘገባ የወጣው ኬሲ-135 ነዳጅ የሚሞላ የአሜሪካ አየር ኃይል አውሮፕላን ባለፈው ሐሙስ በምዕራባዊ ኢራቅ ውስጥ መከስከሱ ከተነገረ በኋላ ነው።
በመካከለኛው ምሥራቅ የአሜሪካንን ወታደራዊ ተልዕኮዎች የሚቆጣጠረው የዩናይትድ ስቴትስ ጦር ኃይል ማዕከላዊ ዕዝ (ሴንትኮም) እንዳረጋገጠው በአደጋው በአውሮፕላኑ ውስጥ የነበሩ ሁሉም ስድስት አባላቱ ሞተዋል።
BBC
5 months ago
" የካሜኒ ስም ይቀጥላል ! "
ሞጅታባ ካሜኒን አዲሱ የኢራን ጠቅላይ መሪ ተደርገው ተሾሙ።
የኢራን ከፍተኛ መንፈሳዊ እና ፖለቲካዊ ሥልጣን ያላቸው ባለሙያዎች ጉባዔ ቀጣዩን የኢራን ጠቅላይ መሪ ሾሟል።
በዚህም የቀድሞው የበላይ መሪ አያቶላ አሊ ካሜኒ ሁለተኛ ልጅ የሆኑትን ሞጅታባ ካሜኒን አዲሱ ጠቅላይ መሪ ሆነዋል።
የ56 ዓመቱ ሞጅታባ ካሜኒ በኢራን ከፍተኛ የፖለቲካ እና የሃይማኖት ስልጣን ያለውን "የበላይ መሪ" ቦታ እንዲይዙ ተመርጠዋል።
ይህ ሹመት የተከናወነው አባታቸው አያቶላ አሊ ካሜኒ በእስራኤል እና በአሜሪካ የአየር ጥቃት መገደላቸውን ተከትሎ ነው።
ምክር ቤቱ ምርጫውን በምስጢር እና በከፍተኛ ጥንቃቄ ሲያካሂድ የቆየ ሲሆን በስተመጨረሻም " የካሜኒ ስም ይቀጥላል " በሚል ሹመቱን ይፋ አድርጓል።
የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ቀደም ብለው የካሜኒ ልጅ ሹመት "ተቀባይነት የሌለው" ሲሉ የገለጹት ሲሆን አዲሱ መሪ ያለ አሜሪካ ፍቃድ ብዙ ሊቆዩ እንደማይችሉ አስጠንቅቀዋል።
አሜሪካ ከሷ ጋር የሚስማማ የኢራን መሪ በመምረጥ በኩል ከፍተኛ ሚና እንደሚኖራት ትራምፕ ተናግረውም ነበር።
tikvahethiopia
ሞጅታባ ካሜኒን አዲሱ የኢራን ጠቅላይ መሪ ተደርገው ተሾሙ።
የኢራን ከፍተኛ መንፈሳዊ እና ፖለቲካዊ ሥልጣን ያላቸው ባለሙያዎች ጉባዔ ቀጣዩን የኢራን ጠቅላይ መሪ ሾሟል።
በዚህም የቀድሞው የበላይ መሪ አያቶላ አሊ ካሜኒ ሁለተኛ ልጅ የሆኑትን ሞጅታባ ካሜኒን አዲሱ ጠቅላይ መሪ ሆነዋል።
የ56 ዓመቱ ሞጅታባ ካሜኒ በኢራን ከፍተኛ የፖለቲካ እና የሃይማኖት ስልጣን ያለውን "የበላይ መሪ" ቦታ እንዲይዙ ተመርጠዋል።
ይህ ሹመት የተከናወነው አባታቸው አያቶላ አሊ ካሜኒ በእስራኤል እና በአሜሪካ የአየር ጥቃት መገደላቸውን ተከትሎ ነው።
ምክር ቤቱ ምርጫውን በምስጢር እና በከፍተኛ ጥንቃቄ ሲያካሂድ የቆየ ሲሆን በስተመጨረሻም " የካሜኒ ስም ይቀጥላል " በሚል ሹመቱን ይፋ አድርጓል።
የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ቀደም ብለው የካሜኒ ልጅ ሹመት "ተቀባይነት የሌለው" ሲሉ የገለጹት ሲሆን አዲሱ መሪ ያለ አሜሪካ ፍቃድ ብዙ ሊቆዩ እንደማይችሉ አስጠንቅቀዋል።
አሜሪካ ከሷ ጋር የሚስማማ የኢራን መሪ በመምረጥ በኩል ከፍተኛ ሚና እንደሚኖራት ትራምፕ ተናግረውም ነበር።
tikvahethiopia
Comments