(ዘ-ሐበሻ ዜና) የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከኢራን ጋር ሊያደርጉት ነው በተባለው አዲስ ስምምነት ዙሪያ፣ የሪፐብሊካን ፓርቲ ታላላቅ ፖለቲከኞች የተለያየ እና የሚጋጭ አቋም እያንጸባረቁ ይገኛሉ። እስካሁን በይፋ የተደረሰ ስምምነትም ሆነ የወጣ ዝርዝር መረጃ ባይኖርም፣ ሊኖር ይችላል የተባለው ስምምነት በፓርቲው ውስጥ ከፍተኛ ክርክር አስነስቷል።
ታዋቂው ሴኔተር ቴድ ክሩዝ በጉዳዩ ላይ ከፍተኛ ስጋት እንዳደረባቸው ገልጸዋል። ሴኔተሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ላይ ባሰፈሩት ጽሁፍ፣ ትራምፕ በኢራን ላይ ጥቃት መክፈታቸው ትክክለኛ እርምጃ ቢሆንም፣ ስምምነቱ ኢራን በቢሊዮን የሚቆጠር ዶላር እንድታገኝ፣ ዩራኒየም እንድታበለጽግ፣ የኒውክሌር መሳሪያ እንድትሰራ እና የሆርሙዝ ባህረ ሰላጤን እንድትቆጣጠር የሚፈቅድ ከሆነ ግን "አስከፊ ስህተት" ይሆናል በማለት አጥብቀው አስጠንቅቀዋል።
በተመሳሳይ ሴኔተር ቶም ቲሊስ ሂደቱ ትርጉም እንደማይሰጣቸው ተናግረዋል። የመከላከያ ሚኒስትሩ ፒት ሄግሴዝ ከሳምንታት በፊት የኢራን መከላከያ ሙሉ በሙሉ መውደሙን እና የኒውክሌር ማዕድኑን በእጅ ማስገባት የጊዜ ጉዳይ ብቻ መሆኑን ተናግረው እንደነበር ያስታወሱት ሴኔተሩ፣ አሁን ላይ የኒውክሌር ማቴሪያሉ በኢራን ውስጥ ሊቀር እንደሚችል የሚጠቁሙ ሀሳቦች ለምን እንደሚነሱ በጥያቄ አቅርበዋል።
በሌላ በኩል ደግሞ ስምምነቱን በአዎንታዊ መልኩ የሚመለከቱ የፓርቲው አባላት አልጠፉም። ኮንግረስማን ቶማስ ማሲ ለኤንቢሲ (NBC) በሰጡት አስተያየት፣ እንደ ሊንድሴይ ግርሃም እና ቴድ ክሩዝ ያሉ ሴኔተሮች ስምምነቱን አጥብቀው የሚቃወሙት ከሆነ፣ ስምምነቱ "በጣም ጥሩ" ሊሆን እንደሚችል ተናግረዋል።
ኮንግረስማን ማሲ ባለፈው ዓመት የአሜሪካ ጦር ያለ ኮንግረሱ ፈቃድ በኢራን ላይ ወታደራዊ እርምጃ እንዳይወስድ የሚከለክል የውሳኔ ሀሳብ አቅርበው እንደነበር ይታወሳል።
እንዲሁም የሴኔቱ አብላጫ ድምጽ አስተባባሪ የሆኑት ጆን ባራሶ፣ የስምምነቱ ዝርዝር ሁኔታ ገና ባይታወቅም፣ የትራምፕ የሀይል እርምጃ እና የአሜሪካ ጥንካሬ ኢራንን ተገዳ ወደ ድርድር ጠረጴዛ እንድትመጣ አድርጓታል በማለት ለሂደቱ ያላቸውን አዎንታዊ አቋም አንጸባርቀዋል።
ታዋቂው ሴኔተር ቴድ ክሩዝ በጉዳዩ ላይ ከፍተኛ ስጋት እንዳደረባቸው ገልጸዋል። ሴኔተሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ላይ ባሰፈሩት ጽሁፍ፣ ትራምፕ በኢራን ላይ ጥቃት መክፈታቸው ትክክለኛ እርምጃ ቢሆንም፣ ስምምነቱ ኢራን በቢሊዮን የሚቆጠር ዶላር እንድታገኝ፣ ዩራኒየም እንድታበለጽግ፣ የኒውክሌር መሳሪያ እንድትሰራ እና የሆርሙዝ ባህረ ሰላጤን እንድትቆጣጠር የሚፈቅድ ከሆነ ግን "አስከፊ ስህተት" ይሆናል በማለት አጥብቀው አስጠንቅቀዋል።
በተመሳሳይ ሴኔተር ቶም ቲሊስ ሂደቱ ትርጉም እንደማይሰጣቸው ተናግረዋል። የመከላከያ ሚኒስትሩ ፒት ሄግሴዝ ከሳምንታት በፊት የኢራን መከላከያ ሙሉ በሙሉ መውደሙን እና የኒውክሌር ማዕድኑን በእጅ ማስገባት የጊዜ ጉዳይ ብቻ መሆኑን ተናግረው እንደነበር ያስታወሱት ሴኔተሩ፣ አሁን ላይ የኒውክሌር ማቴሪያሉ በኢራን ውስጥ ሊቀር እንደሚችል የሚጠቁሙ ሀሳቦች ለምን እንደሚነሱ በጥያቄ አቅርበዋል።
በሌላ በኩል ደግሞ ስምምነቱን በአዎንታዊ መልኩ የሚመለከቱ የፓርቲው አባላት አልጠፉም። ኮንግረስማን ቶማስ ማሲ ለኤንቢሲ (NBC) በሰጡት አስተያየት፣ እንደ ሊንድሴይ ግርሃም እና ቴድ ክሩዝ ያሉ ሴኔተሮች ስምምነቱን አጥብቀው የሚቃወሙት ከሆነ፣ ስምምነቱ "በጣም ጥሩ" ሊሆን እንደሚችል ተናግረዋል።
ኮንግረስማን ማሲ ባለፈው ዓመት የአሜሪካ ጦር ያለ ኮንግረሱ ፈቃድ በኢራን ላይ ወታደራዊ እርምጃ እንዳይወስድ የሚከለክል የውሳኔ ሀሳብ አቅርበው እንደነበር ይታወሳል።
እንዲሁም የሴኔቱ አብላጫ ድምጽ አስተባባሪ የሆኑት ጆን ባራሶ፣ የስምምነቱ ዝርዝር ሁኔታ ገና ባይታወቅም፣ የትራምፕ የሀይል እርምጃ እና የአሜሪካ ጥንካሬ ኢራንን ተገዳ ወደ ድርድር ጠረጴዛ እንድትመጣ አድርጓታል በማለት ለሂደቱ ያላቸውን አዎንታዊ አቋም አንጸባርቀዋል።
26 days ago