11 hours ago
ሕወሃት አዲስ አውዳሚ ጦርነት ሊቀሰቀስ እንደሚችል በማስጠንቀቅ ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ አስቸኳይ ጥሪ አቀረበ።
ህውሃት ከፊታችን አውዳሚ ጦርነት እየመጣ ይገኛል አስወግዱ ሲል ለአለማቀፍ ማህብረሰብ ባሰራጨው ደብዳቤ፣ በኢትዮጵያ ያለው የፖለቲካ ሁኔታ አሳሳቢ ደረጃ ላይ ደርሷል ሲል ገልጿል።
በምርጫ ቦርድ እውቅናው የተሰረዘው ድርጅቱ ግንቦት 26 ቀን 2018 ዓ.ም "ሊቀረፍ የማይችልና አውዳሚ ጦርነትን ለመከላከል የቀረበ አስቸኳይ ጥሪ" በሚል ርዕስ ለዲፕሎማሲያዊ ሚሲዮኖች እና ለዓለም አቀፍ አጋሮች ባሰራጨው የዲፕሎማሲያዊ ማስታወሻ ሀገሪቱ ወደ አዲስ የትጥቅ ግጭት እያመራች መሆኑን አስጠንቅቋል።
እንደ ሕወሃት መግለጫ ከሆነ በአሁኑ ወቅት በሀገሪቱ የውይይት እና የስምምነት መንፈስ እየጠፋ በመምጣቱ በእርሱ ፋንታ "የአንድ ወገን ውሳኔ፣ ማስገደድ እና ወታደራዊ የኃይል እርምጃ" ፖሊሲዎች እየነገሱ መጥተዋል ብሏል። ይህ አካሄድ መቀጠሉ ደግሞ ዳግም የትጥቅ ግጭት መከሰቱ የማይቀሬ እንዲሆን እያደረገው ነው ብሏል።
ይህ ሊቀሰቀስ የሚችለው ጦርነት በኢትዮጵያ ድንበር ብቻ ተወስኖ እንደማይቀር የጠቆመው መግለጫው በአፍሪካ ቀንድ ያለውን ቀጣናዊ ውጥረት እና ለጎረቤት ሀገራት የሚታየውን የጠብ አጫሪነት ዝንባሌ ከግምት ውስጥ በማስገባት፣ ግጭቱ አጠቃላይ ቀጣናውን ሊያናጋና ሰብዓዊ ቀውሱን ሊያባብስ እንደሚችል አመልክቷል።
የፌዴራል መንግሥቱ "ግትር አቋም" ይዟል ሲል የወቀሰው ሕወሃት፣ የትግራይ ክልላዊ መንግሥት ግን አሁንም ለሰላማዊ መፍትሔ ያለውን ቁርጠኝነት ገልጿል።
ከሰሞኑ ከፍተኛ ቁጥር ያለው የትግራይ ወጣቶች ወደ ወታደራዊ የስልጠና ካምፖች መግባታቸውን ሪፖርቶች በተሰሙበት በዚህ ወቅት የወጣው መግለጫ ጨምሮም "ማንኛውም ማህበረሰብ ሊሸከመው የሚችለው የጽናት ገደብ አለው" በሚል በትግራይ ላይ ያለው ጫና መጥበቁን የገለጸው ድርጅቱ፣ ቢሆንም ግን ብቸኛው አማራጭ መንገድ የፖለቲካ ውይይት መሆኑን በጽኑ እንደሚያምን አስታውቋል።
በመጨረሻም ሕወሃት የችግሩን ስር የሰደዱ መንስኤዎች ለመፍታት እንዲቻል፣ በዓለም አቀፉ ማህበረሰብ የሚመራና የሚደገፍ ታማኝ የፖለቲካ ሂደት እንዲጀመርና ለዚህም ዝግጁ መሆኑን በመግለጫው ገልጿል።
Seledadotio
Seledadotio
ህውሃት ከፊታችን አውዳሚ ጦርነት እየመጣ ይገኛል አስወግዱ ሲል ለአለማቀፍ ማህብረሰብ ባሰራጨው ደብዳቤ፣ በኢትዮጵያ ያለው የፖለቲካ ሁኔታ አሳሳቢ ደረጃ ላይ ደርሷል ሲል ገልጿል።
በምርጫ ቦርድ እውቅናው የተሰረዘው ድርጅቱ ግንቦት 26 ቀን 2018 ዓ.ም "ሊቀረፍ የማይችልና አውዳሚ ጦርነትን ለመከላከል የቀረበ አስቸኳይ ጥሪ" በሚል ርዕስ ለዲፕሎማሲያዊ ሚሲዮኖች እና ለዓለም አቀፍ አጋሮች ባሰራጨው የዲፕሎማሲያዊ ማስታወሻ ሀገሪቱ ወደ አዲስ የትጥቅ ግጭት እያመራች መሆኑን አስጠንቅቋል።
እንደ ሕወሃት መግለጫ ከሆነ በአሁኑ ወቅት በሀገሪቱ የውይይት እና የስምምነት መንፈስ እየጠፋ በመምጣቱ በእርሱ ፋንታ "የአንድ ወገን ውሳኔ፣ ማስገደድ እና ወታደራዊ የኃይል እርምጃ" ፖሊሲዎች እየነገሱ መጥተዋል ብሏል። ይህ አካሄድ መቀጠሉ ደግሞ ዳግም የትጥቅ ግጭት መከሰቱ የማይቀሬ እንዲሆን እያደረገው ነው ብሏል።
ይህ ሊቀሰቀስ የሚችለው ጦርነት በኢትዮጵያ ድንበር ብቻ ተወስኖ እንደማይቀር የጠቆመው መግለጫው በአፍሪካ ቀንድ ያለውን ቀጣናዊ ውጥረት እና ለጎረቤት ሀገራት የሚታየውን የጠብ አጫሪነት ዝንባሌ ከግምት ውስጥ በማስገባት፣ ግጭቱ አጠቃላይ ቀጣናውን ሊያናጋና ሰብዓዊ ቀውሱን ሊያባብስ እንደሚችል አመልክቷል።
የፌዴራል መንግሥቱ "ግትር አቋም" ይዟል ሲል የወቀሰው ሕወሃት፣ የትግራይ ክልላዊ መንግሥት ግን አሁንም ለሰላማዊ መፍትሔ ያለውን ቁርጠኝነት ገልጿል።
ከሰሞኑ ከፍተኛ ቁጥር ያለው የትግራይ ወጣቶች ወደ ወታደራዊ የስልጠና ካምፖች መግባታቸውን ሪፖርቶች በተሰሙበት በዚህ ወቅት የወጣው መግለጫ ጨምሮም "ማንኛውም ማህበረሰብ ሊሸከመው የሚችለው የጽናት ገደብ አለው" በሚል በትግራይ ላይ ያለው ጫና መጥበቁን የገለጸው ድርጅቱ፣ ቢሆንም ግን ብቸኛው አማራጭ መንገድ የፖለቲካ ውይይት መሆኑን በጽኑ እንደሚያምን አስታውቋል።
በመጨረሻም ሕወሃት የችግሩን ስር የሰደዱ መንስኤዎች ለመፍታት እንዲቻል፣ በዓለም አቀፉ ማህበረሰብ የሚመራና የሚደገፍ ታማኝ የፖለቲካ ሂደት እንዲጀመርና ለዚህም ዝግጁ መሆኑን በመግለጫው ገልጿል።
Seledadotio
Seledadotio
2 days ago
"ኢትዮጵያ በመከፋፈል ሳይሆን በአንድነት የደመቀ... አገር ሆና እንድትቀጥል ለማየት ነው ምኞታችንና ጸሎታችን!!"
#ethiopia | የዘንድሮውን የ7ኛ ዙር አገራዊ ምርጫ ለመታዘብ የሚያስችለኝን ዕድል አግኝቼ ነበር። እናም በግልና የተለያዩ ተቋማትን ወክለን የመጣን የአገር ውስጥ ታዛቢ ቡድን አባላት ምርጫውን ለመታዘብ ከመጡ የአፍሪካ ኅብረት እና የኢጋድ የታዛቢ ቡድን አባላት ጋር በስካይ ላይት ሆቴል የትውውቅና ሰፋ ያለ የጋራ ውይይት አድርገን ነበር።
በዚህ ውይይት ላይም የኢጋድ የምርጫ ታዛቢ ቡድን መሪና የቀድሞ የኡጋንዳ የቀድሞው ምክትል ፕሬዚደንት የነበሩት ዶ/ር ዋንዲራ ካዚብዌ በምክር መልኩ ለወጣቶች ያነሱት ሐሳብ ቀልቤን ገዛው። እናም ከእኚህ ጉምቱ ፖለቲከኛ አፍሪካዊ እናት ከሐሳባቸው ጥቂት ሰበዞችን ለመምዘዝ ወደድኹ።
በአገራቸው ኡጋንዳ ፖለቲካ ውስጥ የሴቶችን/የእናቶችን የፖለቲካ ተሳትፎ ትርጉም ባለው መንገድ በመቀየር ጉልህ አሻራ ያኖሩት የህክምና ሳይንስን ከሥነ-መንግሥት ትምህርት ጋር ያጣጣሙ እኚህ አፍሪካዊ ምሁር እናት በውይይታችን መካከል እንዲህ አሉን።
"When women lead, even water climbs uphill."
"ሴቶች ሲመሩ ውኃ ሳይቀር እንኳን ሽቅብ ይፈሳል፤" የሚል አፍሪካዊ አባባል አለ።
መቼም ለዚህ አባባል እናንት ኢትዮጵያውያን ሕያው ምስክሮች ናችሁ። ከኢትዮጵያዊቷ ንግሥት ሳባ፣ የዐድዋውን ጦርነት በሴትነት ብልሃት ከመሩት እቴጌ ጣይቱ ድረስ የአገራችሁ የፖለቲካ ታሪክ በሴቶች ጉልህ ተሳትፎና አሻራ የደመቀ ነው።
በእውነት በእነዚህ ጀግኖች እናቶቻችሁ ታሪክ ልትኮሩ፤ ልትደነቁ ይገባችኋል።
ዶ/ር ካዚብዌ ቁጭት በቀላቀለ ስሜት ያነሱትን ሌላኛው የሐሳባቸውን ሰበዝ ለዚህች አጭር ማስታወሻ መደምደሚያ ይሆነኝ ዘንድ መረጥኩት።
እኛ አፍሪካውያን ዲሞክራሲያዊ ሥርዓትን እንደ ሸቀጥ ዕቃ ሙሉ በሙሉ ከምዕራቡ ዓለም ለማስገባት የምናደርገውን ልፋት ቆም ብለን መፈተሽ ይገባናል። ከሌሎች የምንቀበለውን ያህል እኛ አፍሪካውያን ለተቀረው ዓለም ልንሰጠው የምንችላቸው በርካታ ነገሮች አሉን።
አፍሪካ ለሺህ ዓመታት የቆየ የራሷ የሆነ ግዙፍ ታሪክ፤ ገናና ሥልጣኔ፤ በዘመናት ተፈትኖ ያለፈ የዳበረ ባህላዊ የፖለቲካ ሥርዓት ያላት አህጉር ናት። እናንት ኢትዮጵያውያን ደግሞ በዚህ የአኅጉራችን የአፍሪካ የሺህ ዘመናት ታሪክና ባህል ውስጥ የአንበሳውን ድርሻ ትወስዳላችሁ።
ከአክሱም ገናና ሥልጣኔ የቅኝ ገዢዎችንና የተስፋፊዎችን ቅስም እስካንኮታኮተው የዐድዋ ድል ድረስ አኩሪ ታሪክ ያላችሁ ታላቅ ሕዝብ ናችሁ።
አብዛኛው የታሪካችሁ ምዕራፍ ሲገለጽም- የአንድነትን፤ የኅብረትን ኃይል ቀድሞ የተረዳችሁ ጠቢባን ሕዝቦች መሆናችሁን ነው የሚመስክረው። እናም ዛሬ ልዩነታችሁን በማጥበብ አንድነታችሁን አጠናከሩ፤ ኅብረታችሁን አጎልብቱ። አንድነት ኃይል ነው!!
ኢትዮጵያ በመከፋፈል ሳይሆን በአንድነት የደመቀ፤ በጦርነት ሳይሆን በሰላም ያሸበረቀ፤ በጥላቻ ሳይሆን በፍቅር የተዋበ አፍሪካዊ ተምሳሌትነቷንና እናትነቷን ያስመሰከረች አገር ሆና እንድትቀጥል ነው ምኞታችን፤ ተስፋችንና ጸሎታችን።
እግዚአብሔር አፍሪካን ይባርክ፤ አምላክ ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ይባርክ!!
ነገርን ነገር ያነሳዋል እንዲሉ አበው፤ ጠቅላይ ሚ/ር ዶ/ር ዐብይ አሕመድ ወደ ሥልጣን በመጡ ማግሥት- ኢትዮጵያውያን እናቶች ይጸልዩልኛል፤ የእናቶቼ ጸሎታቸውና ምርቃታቸው ያግዘኛል፤ ጉልበት ይሆነኛል። የሚል ቃልን አብዝተን ከአንደበታቸው አንሰማ ነበር። ዛሬስ...?!
ታላቁ መጽሐፍ፤ "የእናት ምርቃት ቤትን ያጸናል፤" እንዲል በእናቶቻችን ምርቃትና ጸሎት የሁላችን ቤት የሆነች ኢትዮጵያ፤ አፍሪካ የአንድነት መሠረቷ ጸንቶና ሰላሟ ተጠብቆ በአንድነት ጸንታ ትኖር ዘንድ በመመኘት ልሰናበት።
ሰላም!!
በተረፈ ወርቁ (ዲ/ን)፤
#ethiopia | የዘንድሮውን የ7ኛ ዙር አገራዊ ምርጫ ለመታዘብ የሚያስችለኝን ዕድል አግኝቼ ነበር። እናም በግልና የተለያዩ ተቋማትን ወክለን የመጣን የአገር ውስጥ ታዛቢ ቡድን አባላት ምርጫውን ለመታዘብ ከመጡ የአፍሪካ ኅብረት እና የኢጋድ የታዛቢ ቡድን አባላት ጋር በስካይ ላይት ሆቴል የትውውቅና ሰፋ ያለ የጋራ ውይይት አድርገን ነበር።
በዚህ ውይይት ላይም የኢጋድ የምርጫ ታዛቢ ቡድን መሪና የቀድሞ የኡጋንዳ የቀድሞው ምክትል ፕሬዚደንት የነበሩት ዶ/ር ዋንዲራ ካዚብዌ በምክር መልኩ ለወጣቶች ያነሱት ሐሳብ ቀልቤን ገዛው። እናም ከእኚህ ጉምቱ ፖለቲከኛ አፍሪካዊ እናት ከሐሳባቸው ጥቂት ሰበዞችን ለመምዘዝ ወደድኹ።
በአገራቸው ኡጋንዳ ፖለቲካ ውስጥ የሴቶችን/የእናቶችን የፖለቲካ ተሳትፎ ትርጉም ባለው መንገድ በመቀየር ጉልህ አሻራ ያኖሩት የህክምና ሳይንስን ከሥነ-መንግሥት ትምህርት ጋር ያጣጣሙ እኚህ አፍሪካዊ ምሁር እናት በውይይታችን መካከል እንዲህ አሉን።
"When women lead, even water climbs uphill."
"ሴቶች ሲመሩ ውኃ ሳይቀር እንኳን ሽቅብ ይፈሳል፤" የሚል አፍሪካዊ አባባል አለ።
መቼም ለዚህ አባባል እናንት ኢትዮጵያውያን ሕያው ምስክሮች ናችሁ። ከኢትዮጵያዊቷ ንግሥት ሳባ፣ የዐድዋውን ጦርነት በሴትነት ብልሃት ከመሩት እቴጌ ጣይቱ ድረስ የአገራችሁ የፖለቲካ ታሪክ በሴቶች ጉልህ ተሳትፎና አሻራ የደመቀ ነው።
በእውነት በእነዚህ ጀግኖች እናቶቻችሁ ታሪክ ልትኮሩ፤ ልትደነቁ ይገባችኋል።
ዶ/ር ካዚብዌ ቁጭት በቀላቀለ ስሜት ያነሱትን ሌላኛው የሐሳባቸውን ሰበዝ ለዚህች አጭር ማስታወሻ መደምደሚያ ይሆነኝ ዘንድ መረጥኩት።
እኛ አፍሪካውያን ዲሞክራሲያዊ ሥርዓትን እንደ ሸቀጥ ዕቃ ሙሉ በሙሉ ከምዕራቡ ዓለም ለማስገባት የምናደርገውን ልፋት ቆም ብለን መፈተሽ ይገባናል። ከሌሎች የምንቀበለውን ያህል እኛ አፍሪካውያን ለተቀረው ዓለም ልንሰጠው የምንችላቸው በርካታ ነገሮች አሉን።
አፍሪካ ለሺህ ዓመታት የቆየ የራሷ የሆነ ግዙፍ ታሪክ፤ ገናና ሥልጣኔ፤ በዘመናት ተፈትኖ ያለፈ የዳበረ ባህላዊ የፖለቲካ ሥርዓት ያላት አህጉር ናት። እናንት ኢትዮጵያውያን ደግሞ በዚህ የአኅጉራችን የአፍሪካ የሺህ ዘመናት ታሪክና ባህል ውስጥ የአንበሳውን ድርሻ ትወስዳላችሁ።
ከአክሱም ገናና ሥልጣኔ የቅኝ ገዢዎችንና የተስፋፊዎችን ቅስም እስካንኮታኮተው የዐድዋ ድል ድረስ አኩሪ ታሪክ ያላችሁ ታላቅ ሕዝብ ናችሁ።
አብዛኛው የታሪካችሁ ምዕራፍ ሲገለጽም- የአንድነትን፤ የኅብረትን ኃይል ቀድሞ የተረዳችሁ ጠቢባን ሕዝቦች መሆናችሁን ነው የሚመስክረው። እናም ዛሬ ልዩነታችሁን በማጥበብ አንድነታችሁን አጠናከሩ፤ ኅብረታችሁን አጎልብቱ። አንድነት ኃይል ነው!!
ኢትዮጵያ በመከፋፈል ሳይሆን በአንድነት የደመቀ፤ በጦርነት ሳይሆን በሰላም ያሸበረቀ፤ በጥላቻ ሳይሆን በፍቅር የተዋበ አፍሪካዊ ተምሳሌትነቷንና እናትነቷን ያስመሰከረች አገር ሆና እንድትቀጥል ነው ምኞታችን፤ ተስፋችንና ጸሎታችን።
እግዚአብሔር አፍሪካን ይባርክ፤ አምላክ ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ይባርክ!!
ነገርን ነገር ያነሳዋል እንዲሉ አበው፤ ጠቅላይ ሚ/ር ዶ/ር ዐብይ አሕመድ ወደ ሥልጣን በመጡ ማግሥት- ኢትዮጵያውያን እናቶች ይጸልዩልኛል፤ የእናቶቼ ጸሎታቸውና ምርቃታቸው ያግዘኛል፤ ጉልበት ይሆነኛል። የሚል ቃልን አብዝተን ከአንደበታቸው አንሰማ ነበር። ዛሬስ...?!
ታላቁ መጽሐፍ፤ "የእናት ምርቃት ቤትን ያጸናል፤" እንዲል በእናቶቻችን ምርቃትና ጸሎት የሁላችን ቤት የሆነች ኢትዮጵያ፤ አፍሪካ የአንድነት መሠረቷ ጸንቶና ሰላሟ ተጠብቆ በአንድነት ጸንታ ትኖር ዘንድ በመመኘት ልሰናበት።
ሰላም!!
በተረፈ ወርቁ (ዲ/ን)፤
16 days ago
በአይራብ ዶኔሽን እና በጃተኒ አሊ ፋውንዴሽን የተዘጋጀው ይፋዊ የዲጂታል ገቢ ማሰባሰቢያ መርሃ-ግብር ሊካሄድ ነው።
👉ተቋማቱ የጋራ ስምምነት ተፈራረሙ
በአይራብ ዶኔሽን እና በጃተኒ አሊ ፋውንዴሽን በጋራ የተዘጋጀው ይፋዊ የገቢ ማሰባሰቢያ የመክፈቻ ፕሮግራም በቅርቡ እንደሚካሄድ የተገለጸ ሲሆን፣ ሁለቱ ተቋማትም አብረው ለመሥራት የሚያስችላቸውን የጋራ ስምምነት በይፋ ተፈራርመዋል።
ይህ ልዩ መርሃ-ግብር ደህንነቱ በተጠበቀ፣ ግልጽነት ባለው እና በዘመናዊ ቴክኖሎጂ በተደገፉ ዲጂታል የለጋሽነት መፍትሄዎች አማካኝነት፣ ተፅዕኖ ፈጣሪ ሰብአዊ እና ማህበረሰባዊ እገዛዎችን በዘላቂነት ለመደገፍ ያለመ ስትራቴጂካዊ የገቢ ማሰባሰብ አጋርነት መጀመሩን አብስረዋል።
በዕለቱም አይራብ ዶኔሽን የሀገር ውስጥና የውጭ ሀገር ለጋሾች በቴሌብር ሱፐር አፕ እና በአይራብ ዶኔሽን ድረ-ገጽ አማካኝነት በቀላሉና በአስተማማኝ ሁኔታ መዋጮ ማድረግ የሚችሉበትን ምቹ ዲጂታል አሰራር በጉልህ የሚያሳይ ይሆናል።
የአይራብ ቴክ ሶሉሽን ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር (AYRAB TECH SOLUTION PLC) መስራች አቶ ቢኒያም ፈቃዱ እና የጃተኒ አሊ ፋውንዴሽን ዋና ስራ አስፈፃሚ ዶክተር መሌቻ ሎጄ ህዝቡ እና የሚመለከተው አካል ሁሉ በዚህ ሰብአዊ ስራ ላይ ከጎናቸው እንዲሆንና አጋርነቱን እንዲያጠናክር ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።
ጃታኒ አሊ ፋውንዴሽን በአርቆ አሳቢው ሻለቃ ጃታኒ አሊ ማስታወሻነት የተመሰረተ ሲሆን፣ ማህበረሰቡ ራሱን እንዲችል፣ ጠንካራ የሆነ ማህበረሰብ እንዲገነባ እና ዘላቂ ልማት እንዲፈጠር በትምህርት፣ በውሃ፣ በጤና እና በማህበረሰብ አቅም ግንባታ ላይ በትጋት እየሰራ ነው።
ዛሬ የፋውንዴሽኑ ዋና ስራ አስፈፃሚና በተለያዩ ሀገር የሃላፊነት ቦታዎች የሚያገለግሉ ብዙ ግለሰቦች ሻለቃ ጃታኒ አሊ በተቋቋመው ትምህርት ቤት የተማሩ ሲሆን፣ ይህም የፋውንዴሽኑ ትውልድ የሚቀይር ራዕይ ህያው ማስረጃ ነው።
የእርስዎ ድጋፍ አንድ ልጅ እንዲማር፣ አንድ ቤተሰብ ተስፋ እንዲያገኝ እና አንድ ማህበረሰብ በራሱ እግር እንዲቆም ያግዛል።
ዛሬ ይቀላቀሉ ፣ ይደግፉ ፣ዘላቂ ለውጥ ይፍጠሩ። ሲሉ ጥሪያቸውንም አስተላልፈዋል።
እንዲሁም: በቴሌብር ሱፐር አፕ ላይ በሚገኘው አይራብ(AYRAB) አፕ ላይ እና በአይራብ ዶኔሽን ( https://donate.ayrabtech.c... ) ሊንክ በመግባት በቀላሉ በሃገር ውስጥም ይሁን ከሃገር ውጪ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን እና የኢትዮዽያ ወዳጆች በቀላሉ የፈለጉትን እና የቻሉትን ያህል መለገስ የሚችሉ መሆኑን አሳውቀዋል።
ይህንን ትልቅ ሰብአዊ እቅድ በይፋ ለመጀመር በሚሰናዳው በዚሁ ደማቅ መርሃ-ግብር ላይ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች፣ በጎ አድራጊዎች፣ የቢዝነስ መሪዎች፣ የሶሻል ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች፣ ታዋቂ የኢትዮጵያ ስብዕናዎች እና ከተለያዩ ዘርፎች የተወጣጡ ደጋፊዎች እንደሚገኙ ታውቋል።
👉ተቋማቱ የጋራ ስምምነት ተፈራረሙ
በአይራብ ዶኔሽን እና በጃተኒ አሊ ፋውንዴሽን በጋራ የተዘጋጀው ይፋዊ የገቢ ማሰባሰቢያ የመክፈቻ ፕሮግራም በቅርቡ እንደሚካሄድ የተገለጸ ሲሆን፣ ሁለቱ ተቋማትም አብረው ለመሥራት የሚያስችላቸውን የጋራ ስምምነት በይፋ ተፈራርመዋል።
ይህ ልዩ መርሃ-ግብር ደህንነቱ በተጠበቀ፣ ግልጽነት ባለው እና በዘመናዊ ቴክኖሎጂ በተደገፉ ዲጂታል የለጋሽነት መፍትሄዎች አማካኝነት፣ ተፅዕኖ ፈጣሪ ሰብአዊ እና ማህበረሰባዊ እገዛዎችን በዘላቂነት ለመደገፍ ያለመ ስትራቴጂካዊ የገቢ ማሰባሰብ አጋርነት መጀመሩን አብስረዋል።
በዕለቱም አይራብ ዶኔሽን የሀገር ውስጥና የውጭ ሀገር ለጋሾች በቴሌብር ሱፐር አፕ እና በአይራብ ዶኔሽን ድረ-ገጽ አማካኝነት በቀላሉና በአስተማማኝ ሁኔታ መዋጮ ማድረግ የሚችሉበትን ምቹ ዲጂታል አሰራር በጉልህ የሚያሳይ ይሆናል።
የአይራብ ቴክ ሶሉሽን ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር (AYRAB TECH SOLUTION PLC) መስራች አቶ ቢኒያም ፈቃዱ እና የጃተኒ አሊ ፋውንዴሽን ዋና ስራ አስፈፃሚ ዶክተር መሌቻ ሎጄ ህዝቡ እና የሚመለከተው አካል ሁሉ በዚህ ሰብአዊ ስራ ላይ ከጎናቸው እንዲሆንና አጋርነቱን እንዲያጠናክር ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።
ጃታኒ አሊ ፋውንዴሽን በአርቆ አሳቢው ሻለቃ ጃታኒ አሊ ማስታወሻነት የተመሰረተ ሲሆን፣ ማህበረሰቡ ራሱን እንዲችል፣ ጠንካራ የሆነ ማህበረሰብ እንዲገነባ እና ዘላቂ ልማት እንዲፈጠር በትምህርት፣ በውሃ፣ በጤና እና በማህበረሰብ አቅም ግንባታ ላይ በትጋት እየሰራ ነው።
ዛሬ የፋውንዴሽኑ ዋና ስራ አስፈፃሚና በተለያዩ ሀገር የሃላፊነት ቦታዎች የሚያገለግሉ ብዙ ግለሰቦች ሻለቃ ጃታኒ አሊ በተቋቋመው ትምህርት ቤት የተማሩ ሲሆን፣ ይህም የፋውንዴሽኑ ትውልድ የሚቀይር ራዕይ ህያው ማስረጃ ነው።
የእርስዎ ድጋፍ አንድ ልጅ እንዲማር፣ አንድ ቤተሰብ ተስፋ እንዲያገኝ እና አንድ ማህበረሰብ በራሱ እግር እንዲቆም ያግዛል።
ዛሬ ይቀላቀሉ ፣ ይደግፉ ፣ዘላቂ ለውጥ ይፍጠሩ። ሲሉ ጥሪያቸውንም አስተላልፈዋል።
እንዲሁም: በቴሌብር ሱፐር አፕ ላይ በሚገኘው አይራብ(AYRAB) አፕ ላይ እና በአይራብ ዶኔሽን ( https://donate.ayrabtech.c... ) ሊንክ በመግባት በቀላሉ በሃገር ውስጥም ይሁን ከሃገር ውጪ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን እና የኢትዮዽያ ወዳጆች በቀላሉ የፈለጉትን እና የቻሉትን ያህል መለገስ የሚችሉ መሆኑን አሳውቀዋል።
ይህንን ትልቅ ሰብአዊ እቅድ በይፋ ለመጀመር በሚሰናዳው በዚሁ ደማቅ መርሃ-ግብር ላይ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች፣ በጎ አድራጊዎች፣ የቢዝነስ መሪዎች፣ የሶሻል ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች፣ ታዋቂ የኢትዮጵያ ስብዕናዎች እና ከተለያዩ ዘርፎች የተወጣጡ ደጋፊዎች እንደሚገኙ ታውቋል።
16 days ago
በአይራብ ዶኔሽን እና በጃተኒ አሊ ፋውንዴሽን የተዘጋጀው ይፋዊ የዲጂታል ገቢ ማሰባሰቢያ መርሃ-ግብር ሊካሄድ ነው
📌ተቋማቱ የጋራ ስምምነት ተፈራረሙ
#ethiopia | በአይራብ ዶኔሽን እና በጃተኒ አሊ ፋውንዴሽን በጋራ የተዘጋጀው ይፋዊ የገቢ ማሰባሰቢያ የመክፈቻ ፕሮግራም በቅርቡ እንደሚካሄድ የተገለጸ ሲሆን፣ ሁለቱ ተቋማትም አብረው ለመሥራት የሚያስችላቸውን የጋራ ስምምነት በይፋ ተፈራርመዋል።
ይህ ልዩ መርሃ-ግብር ደህንነቱ በተጠበቀ፣ ግልጽነት ባለው እና በዘመናዊ ቴክኖሎጂ በተደገፉ ዲጂታል የለጋሽነት መፍትሄዎች አማካኝነት፣ ተፅዕኖ ፈጣሪ ሰብአዊ እና ማህበረሰባዊ እገዛዎችን በዘላቂነት ለመደገፍ ያለመ ስትራቴጂካዊ የገቢ ማሰባሰብ አጋርነት መጀመሩን አብስረዋል።
በዕለቱም አይራብ ዶኔሽን የሀገር ውስጥና የውጭ ሀገር ለጋሾች በቴሌብር ሱፐር አፕ እና በአይራብ ዶኔሽን ድረ-ገጽ አማካኝነት በቀላሉና በአስተማማኝ ሁኔታ መዋጮ ማድረግ የሚችሉበትን ምቹ ዲጂታል አሰራር በጉልህ የሚያሳይ ይሆናል።
የአይራብ ቴክ ሶሉሽን ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር (AYRAB TECH SOLUTION PLC) መስራች አቶ ቢኒያም ፈቃዱ እና የጃተኒ አሊ ፋውንዴሽን ዋና ስራ አስፈፃሚ ዶክተር መሌቻ ሎጄ ህዝቡ እና የሚመለከተው አካል ሁሉ በዚህ ሰብአዊ ስራ ላይ ከጎናቸው እንዲሆንና አጋርነቱን እንዲያጠናክር ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።
ጃታኒ አሊ ፋውንዴሽን በአርቆ አሳቢው ሻለቃ ጃታኒ አሊ ማስታወሻነት የተመሰረተ ሲሆን፣ ማህበረሰቡ ራሱን እንዲችል፣ ጠንካራ የሆነ ማህበረሰብ እንዲገነባ እና ዘላቂ ልማት እንዲፈጠር በትምህርት፣ በውሃ፣ በጤና እና በማህበረሰብ አቅም ግንባታ ላይ በትጋት እየሰራ ነው።
ዛሬ የፋውንዴሽኑ ዋና ስራ አስፈፃሚና በተለያዩ ሀገር የሃላፊነት ቦታዎች የሚያገለግሉ ብዙ ግለሰቦች ሻለቃ ጃታኒ አሊ በተቋቋመው ትምህርት ቤት የተማሩ ሲሆን፣ ይህም የፋውንዴሽኑ ትውልድ የሚቀይር ራዕይ ህያው ማስረጃ ነው።
የእርስዎ ድጋፍ አንድ ልጅ እንዲማር፣ አንድ ቤተሰብ ተስፋ እንዲያገኝ እና አንድ ማህበረሰብ በራሱ እግር እንዲቆም ያግዛል።
ዛሬ ይቀላቀሉ ፣ ይደግፉ ፣ዘላቂ ለውጥ ይፍጠሩ። ሲሉ ጥሪያቸውንም አስተላልፈዋል።
እንዲሁም: በቴሌብር ሱፐር አፕ ላይ በሚገኘው አይራብ(AYRAB) አፕ ላይ እና በአይራብ ዶኔሽን ( https://donate.ayrabtech.c... ) ሊንክ በመግባት በቀላሉ በሃገር ውስጥም ይሁን ከሃገር ውጪ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን እና የኢትዮዽያ ወዳጆች በቀላሉ የፈለጉትን እና የቻሉትን ያህል መለገስ የሚችሉ መሆኑን አሳውቀዋል።
ይህንን ትልቅ ሰብአዊ እቅድ በይፋ ለመጀመር በሚሰናዳው በዚሁ ደማቅ መርሃ-ግብር ላይ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች፣ በጎ አድራጊዎች፣ የቢዝነስ መሪዎች፣ የሶሻል ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች፣ ታዋቂ የኢትዮጵያ ስብዕናዎች እና ከተለያዩ ዘርፎች የተወጣጡ ደጋፊዎች እንደሚገኙ ታውቋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#ethiopia #ayrabdonation #jatanialifoundation #digitalfundraising #techforgood #humanitarianaid #telebirr #addisababa #socialimpact #ethiopiannews
📌ተቋማቱ የጋራ ስምምነት ተፈራረሙ
#ethiopia | በአይራብ ዶኔሽን እና በጃተኒ አሊ ፋውንዴሽን በጋራ የተዘጋጀው ይፋዊ የገቢ ማሰባሰቢያ የመክፈቻ ፕሮግራም በቅርቡ እንደሚካሄድ የተገለጸ ሲሆን፣ ሁለቱ ተቋማትም አብረው ለመሥራት የሚያስችላቸውን የጋራ ስምምነት በይፋ ተፈራርመዋል።
ይህ ልዩ መርሃ-ግብር ደህንነቱ በተጠበቀ፣ ግልጽነት ባለው እና በዘመናዊ ቴክኖሎጂ በተደገፉ ዲጂታል የለጋሽነት መፍትሄዎች አማካኝነት፣ ተፅዕኖ ፈጣሪ ሰብአዊ እና ማህበረሰባዊ እገዛዎችን በዘላቂነት ለመደገፍ ያለመ ስትራቴጂካዊ የገቢ ማሰባሰብ አጋርነት መጀመሩን አብስረዋል።
በዕለቱም አይራብ ዶኔሽን የሀገር ውስጥና የውጭ ሀገር ለጋሾች በቴሌብር ሱፐር አፕ እና በአይራብ ዶኔሽን ድረ-ገጽ አማካኝነት በቀላሉና በአስተማማኝ ሁኔታ መዋጮ ማድረግ የሚችሉበትን ምቹ ዲጂታል አሰራር በጉልህ የሚያሳይ ይሆናል።
የአይራብ ቴክ ሶሉሽን ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር (AYRAB TECH SOLUTION PLC) መስራች አቶ ቢኒያም ፈቃዱ እና የጃተኒ አሊ ፋውንዴሽን ዋና ስራ አስፈፃሚ ዶክተር መሌቻ ሎጄ ህዝቡ እና የሚመለከተው አካል ሁሉ በዚህ ሰብአዊ ስራ ላይ ከጎናቸው እንዲሆንና አጋርነቱን እንዲያጠናክር ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።
ጃታኒ አሊ ፋውንዴሽን በአርቆ አሳቢው ሻለቃ ጃታኒ አሊ ማስታወሻነት የተመሰረተ ሲሆን፣ ማህበረሰቡ ራሱን እንዲችል፣ ጠንካራ የሆነ ማህበረሰብ እንዲገነባ እና ዘላቂ ልማት እንዲፈጠር በትምህርት፣ በውሃ፣ በጤና እና በማህበረሰብ አቅም ግንባታ ላይ በትጋት እየሰራ ነው።
ዛሬ የፋውንዴሽኑ ዋና ስራ አስፈፃሚና በተለያዩ ሀገር የሃላፊነት ቦታዎች የሚያገለግሉ ብዙ ግለሰቦች ሻለቃ ጃታኒ አሊ በተቋቋመው ትምህርት ቤት የተማሩ ሲሆን፣ ይህም የፋውንዴሽኑ ትውልድ የሚቀይር ራዕይ ህያው ማስረጃ ነው።
የእርስዎ ድጋፍ አንድ ልጅ እንዲማር፣ አንድ ቤተሰብ ተስፋ እንዲያገኝ እና አንድ ማህበረሰብ በራሱ እግር እንዲቆም ያግዛል።
ዛሬ ይቀላቀሉ ፣ ይደግፉ ፣ዘላቂ ለውጥ ይፍጠሩ። ሲሉ ጥሪያቸውንም አስተላልፈዋል።
እንዲሁም: በቴሌብር ሱፐር አፕ ላይ በሚገኘው አይራብ(AYRAB) አፕ ላይ እና በአይራብ ዶኔሽን ( https://donate.ayrabtech.c... ) ሊንክ በመግባት በቀላሉ በሃገር ውስጥም ይሁን ከሃገር ውጪ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን እና የኢትዮዽያ ወዳጆች በቀላሉ የፈለጉትን እና የቻሉትን ያህል መለገስ የሚችሉ መሆኑን አሳውቀዋል።
ይህንን ትልቅ ሰብአዊ እቅድ በይፋ ለመጀመር በሚሰናዳው በዚሁ ደማቅ መርሃ-ግብር ላይ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች፣ በጎ አድራጊዎች፣ የቢዝነስ መሪዎች፣ የሶሻል ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች፣ ታዋቂ የኢትዮጵያ ስብዕናዎች እና ከተለያዩ ዘርፎች የተወጣጡ ደጋፊዎች እንደሚገኙ ታውቋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#ethiopia #ayrabdonation #jatanialifoundation #digitalfundraising #techforgood #humanitarianaid #telebirr #addisababa #socialimpact #ethiopiannews
16 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) በካሊፎርኒያ ግዛት በሳን ዲዬጎ ከተማ በሚገኘው ታላቁ መስጂድ ላይ የተፈጸመውን አሰቃቂ ጥቃት ተከትሎ፣ የሳን ዲዬጎ የካቶሊክ ዲዮሴስ ከሙስሊሙ ማህበረሰብ ጋር በኅብረት እና በጸሎት አብሮ እንደሚቆም በይፋ አስታውቋል። የዲዮሴሱ ቢሾፍ ማይክል ፋም በዛሬው ዕለት ባወጡት መግለጫ፣ ድርጊቱን ምክንያት አልባ እና ዘግናኝ የጥቃት ድርጊት ሲሉ የኮነኑት ሲሆን፤ ለተጎጂ ቤተሰቦች እና ለመላው የሙስሊም ማህበረሰብ ያላቸውን ጥልቅ መረዳት፣ አጋርነት እና ልባዊ ጸሎት አቅርበዋል።
ቢሾፍ ፋም በመግለጫቸው ላይ እንዳሰፈሩት፣ ጥቃቱ የተፈጸመበት የሳን ዲዬጎ እስላማዊ ማዕከል በተለይም ስደተኞችን በመደገፍ እና ፍትህን በማስፈን ረገድ ለረጅም ጊዜ አብሮአቸው የሠራ የቆየ የቅርብ አጋራቸው ነው። የአምልኮ ሥፍራዎች ሁልጊዜም የሰላም፣ የደህንነት እና የጸሎት መጠለያዎች መሆን እንዳለባቸው የጠቆሙት ቢሾፉ፣ በአንድ የእምነት ማህበረሰብ ላይ የሚሰነዘር ጥቃት በሰው ልጅ የተቀደሰ ክብር ላይ የተሰነዘረ ጥቃት መሆኑን አጽንኦት ሰጥተዋል።
በአሁኑ ወቅት የወጡ ዘ-ሐበሻ ያሰባሰባቸው ወቅታዊ መረጃዎች እንደሚያመለክቱት፣ በዚህ አሰቃቂ ጥቃት የጥበቃ ሰራተኛውን ጨምሮ የሦስት ንፁሃን ዜጎች ሕይወት አልፏል። የሳን ዲዬጎ ፖሊስ አዛዥ ስኮት ዋህል እንደገለጹት፣ ሕይወቱን የሰጠው ጥበቃ ሰራተኛ በወቅቱ ባሳየው እጅግ አስደናቂ የጀግንነት ተጋድሎ የብዙዎችን ሕይወት ማዳን ችሏል። ጥቃቱን ፈጽመዋል ተብለው የተጠረጠሩት የ17 እና የ18 ዓመት ሁለት ታዳጊዎች ከመስጂዱ አቅራቢያ በቆመ መኪና ውስጥ ራሳቸውን አጥፍተው ሞተው ተገኝተዋል።
ከተባባሪዎቹ መካከል አንዱ የ17 ዓመቱ ኬን ክላርክ መሆኑ የተረጋገጠ ሲሆን፣ ጥቃቱ ከመፈጸሙ ከሰዓታት በፊት እናቱ ልጇ፣ መኪናዋ እና ሦስት ገዳይ መሣሪያዎች አብረው መጥፋታቸውን ለፖሊስ አመልክታ ነበር። በአሁኑ ሰዓት የሕግ አስከባሪ አካላት ጥቃቱን የጥላቻ ወንጀል በማድረግ ምርመራቸውን በስፋት ቀጥለዋል። ለጥቃቱ ጥቅም ላይ ከዋሉት መሣሪያዎች በአንዱ ላይ የጥላቻ ንግግሮች ተፅፈው የተገኙ ሲሆን፣ ከተጠርጣሪዎቹ በአንዱ ቤት ውስጥ ደግሞ ስለ ዘር የበላይነት እና ኩራት የሚናገር የራስ ማጥፊያ ማስታወሻ መገኘቱን የደህንነት ባለሥልጣናት ለሲኤንኤን አረጋግጠዋል።
ቢሾፍ ፋም በመግለጫቸው ላይ እንዳሰፈሩት፣ ጥቃቱ የተፈጸመበት የሳን ዲዬጎ እስላማዊ ማዕከል በተለይም ስደተኞችን በመደገፍ እና ፍትህን በማስፈን ረገድ ለረጅም ጊዜ አብሮአቸው የሠራ የቆየ የቅርብ አጋራቸው ነው። የአምልኮ ሥፍራዎች ሁልጊዜም የሰላም፣ የደህንነት እና የጸሎት መጠለያዎች መሆን እንዳለባቸው የጠቆሙት ቢሾፉ፣ በአንድ የእምነት ማህበረሰብ ላይ የሚሰነዘር ጥቃት በሰው ልጅ የተቀደሰ ክብር ላይ የተሰነዘረ ጥቃት መሆኑን አጽንኦት ሰጥተዋል።
በአሁኑ ወቅት የወጡ ዘ-ሐበሻ ያሰባሰባቸው ወቅታዊ መረጃዎች እንደሚያመለክቱት፣ በዚህ አሰቃቂ ጥቃት የጥበቃ ሰራተኛውን ጨምሮ የሦስት ንፁሃን ዜጎች ሕይወት አልፏል። የሳን ዲዬጎ ፖሊስ አዛዥ ስኮት ዋህል እንደገለጹት፣ ሕይወቱን የሰጠው ጥበቃ ሰራተኛ በወቅቱ ባሳየው እጅግ አስደናቂ የጀግንነት ተጋድሎ የብዙዎችን ሕይወት ማዳን ችሏል። ጥቃቱን ፈጽመዋል ተብለው የተጠረጠሩት የ17 እና የ18 ዓመት ሁለት ታዳጊዎች ከመስጂዱ አቅራቢያ በቆመ መኪና ውስጥ ራሳቸውን አጥፍተው ሞተው ተገኝተዋል።
ከተባባሪዎቹ መካከል አንዱ የ17 ዓመቱ ኬን ክላርክ መሆኑ የተረጋገጠ ሲሆን፣ ጥቃቱ ከመፈጸሙ ከሰዓታት በፊት እናቱ ልጇ፣ መኪናዋ እና ሦስት ገዳይ መሣሪያዎች አብረው መጥፋታቸውን ለፖሊስ አመልክታ ነበር። በአሁኑ ሰዓት የሕግ አስከባሪ አካላት ጥቃቱን የጥላቻ ወንጀል በማድረግ ምርመራቸውን በስፋት ቀጥለዋል። ለጥቃቱ ጥቅም ላይ ከዋሉት መሣሪያዎች በአንዱ ላይ የጥላቻ ንግግሮች ተፅፈው የተገኙ ሲሆን፣ ከተጠርጣሪዎቹ በአንዱ ቤት ውስጥ ደግሞ ስለ ዘር የበላይነት እና ኩራት የሚናገር የራስ ማጥፊያ ማስታወሻ መገኘቱን የደህንነት ባለሥልጣናት ለሲኤንኤን አረጋግጠዋል።
16 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) በካሊፎርኒያ ግዛት ሳን ዲዬጎ በሚገኘው ትልቁ መስጂድ (የሳን ዲዬጎ እስላማዊ ማዕከል) ላይ ሰኞ ዕለት ተከስቶ የሦስት ሰዎችን ሕይወት የቀጠፈውንና ፖሊስ "የጥላቻ ወንጀል" ሲል የፈረጀውን አስደንጋጭ የተኩስ ጥቃት የፈጸሙት ግለሰቦች ማንነት እና የጥቃቱ ዝርዝር መረጃዎች ወጥተዋል።
ባለሥልጣናቱ እንዳረጋገጡት፣ ጥቃቱን የሰነዘሩት የ17 ዓመት ታዳጊ እና የ18 ዓመት ወጣት ሲሆኑ፣ ሁለቱም ከድርጊቱ በኋላ ከመስጂዱ ብዙም በማይርቅ መንገድ ላይ በቆመ መኪና ውስጥ ራሳቸውን በጥይት አጥፍተው ሞተው ተገኝተዋል።
የሕግ አስከባሪ አካላት በጀመሩት ምርመራ መሰረት፣ ጥቃቱን ለመፈጸም ጥቅም ላይ ከዋሉት መሣሪያዎች በአንዱ ላይ "የጥላቻ ንግግሮች" ተፅፈው የተገኙ ሲሆን፣ በአንዱ ተጠርጣሪ ወላጆች ቤት ውስጥ ደግሞ "ስለ ዘር የበላይነት እና ኩራት" የሚናገር የራስ ማጥፊያ ማስታወሻ ወይም ስንብት ደብዳቤ ተገኝቷል። የሳን ዲዬጎ ፖሊስ አዛዥ ስኮት ዋህል እንዳሉት፣ በደብዳቤው ላይ ለየት ያለ ተለይቶ የተጠቀሰ ተቋም ወይም ቦታ ባይኖርም፣ በአጠቃላይ በእስልምና እና በተለያዩ ወገኖች ላይ ያነጣጠረ ሰፊ የጥላቻ መልዕክት የያዘ ነው።
የሳን ዲዬጎ ፖሊስ አዛዥ ስኮት ዋህል እንደገለጹት፣ ጥቃቱ ከመፈጸሙ ከሁለት ሰዓት በፊት የ17 ዓመቱ ተጠርጣሪ ኬን ክላርክ እናት ለፖሊስ ደውላ ነበር። እናትየው ልጇ፣ መኪናው እንዲሁም በቤት ውስጥ የነበሩ በርካታ መሣሪያዎች መጥፋታቸውን ገልጻ፣ ልጇ ራሱን የማጥፋት ስጋት እንዳለበትና የወታደራዊ መለዮ የለበሰ ሌላ ጓደኛ አብሮት እንዳለ ለፖሊስ ጥቆማ ሰጥታ ነበር። ይህ ጥቆማ ፖሊስን ወደ ከፍተኛ ክትትል ቢያስገባውም፣ ታጣቂዎቹ ግን እኩይ ዓላማቸውን ከመፈጸም አልተገቱም።
ፖሊስ ስፍራው ላይ ሲደርስ የሦስት ሰዎችን አስከሬን ከመስጂዱ ውጪ ያገኘ ሲሆን፣ እስካሁን የሟቾች ስም ይፋ አልተደረገም። ሆኖም ግን ከተገደሉት መካከል አንዱ የመስጂዱ ጥበቃ ሰራተኛ መሆኑ ታውቋል። ፖሊስ የጥበቃ ሰራተኛው ያደረገው ተጋድሎ "ጀግንነት የተሞላበት እና የብዙዎችን ሕይወት የታደገ" ሲል አወድሶታል። ታጣቂዎቹ ሽጉጥ፣ ሾትጋን እና ጠመንጃ ይዘው እንደነበርም ከፖሊስ የራዲዮ መገናኛ ዝርዝሮች ታውቋል።
ማንነቱ የተለየው የ17 ዓመቱ ኬን ክላርክ፣ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱን በኦንላይን የሚከታተል የነጻ ትግል ስፖርት ተጫዋች ነበር። ከ2024 እስከ 2025 ባለው ጊዜ ውስጥ በማዲሰን ከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የትግል ቡድን አባል የነበረ ሲሆን፣ በአንድ ወቅት በውድድር አንደኛ ወጥቶ ሽልማት ጭምር አሸንፎ ነበር። በልጅነቱ (እ.ኤ.አ በ2015) ከፈጸመው የአካል ጥቃት በስተቀር ምንም ዓይነት የዲስፕሊን ጉድለት ታሪክ የሌለው ተማሪ ነበር።
የኬን ክላርክ አያቶች ለሲኤንኤን ሰጡት ቃል፣ በድርጊቱ እጅግ ድንጋጤ ውስጥ መሆናቸውን ገልጸው "በተፈጠረው ነገር በጣም እናዝናለን" ብለዋል። የቀድሞ የትግል ስፖርት ጓደኞቹም ታዳጊው ከተቀረው ቡድን ጋር ለመላመድ እና ጓደኛ ለማፍራት የሚጥር "ጥሩ ልጅ" መስሎ ይታይ እንደነበርና እንዲህ ያለ እስላማዊ ጥላቻ ወይም የዘረኝነት ስሜት ሲያንጸባርቅ ሰምተውት እንደማያውቁ በግርምት ተናግረዋል።
የፌደራል ምርመራ ቢሮ (FBI) ከሳን ዲዬጎ ፖሊስ ጋር በመሆን የተጠርጣሪዎቹን ቤተሰቦች እና ጓደኞች እየመረመረ ሲሆን፣ ከመስጂዱ የደህንነት ካሜራዎች የተገኙ በርካታ ማስረጃዎችን እያጣራ ይገኛል። ፖሊስ አዛዥ ዋህል ሁኔታውን ሲገልጹ፦ "ይህ ለአንድ ነፃ ማህበረሰብ፣ ለከተማችን እና ለህዝባችን ፍጹም አስከፊ ቅዠት ነው" ብለዋል።
ባለሥልጣናቱ እንዳረጋገጡት፣ ጥቃቱን የሰነዘሩት የ17 ዓመት ታዳጊ እና የ18 ዓመት ወጣት ሲሆኑ፣ ሁለቱም ከድርጊቱ በኋላ ከመስጂዱ ብዙም በማይርቅ መንገድ ላይ በቆመ መኪና ውስጥ ራሳቸውን በጥይት አጥፍተው ሞተው ተገኝተዋል።
የሕግ አስከባሪ አካላት በጀመሩት ምርመራ መሰረት፣ ጥቃቱን ለመፈጸም ጥቅም ላይ ከዋሉት መሣሪያዎች በአንዱ ላይ "የጥላቻ ንግግሮች" ተፅፈው የተገኙ ሲሆን፣ በአንዱ ተጠርጣሪ ወላጆች ቤት ውስጥ ደግሞ "ስለ ዘር የበላይነት እና ኩራት" የሚናገር የራስ ማጥፊያ ማስታወሻ ወይም ስንብት ደብዳቤ ተገኝቷል። የሳን ዲዬጎ ፖሊስ አዛዥ ስኮት ዋህል እንዳሉት፣ በደብዳቤው ላይ ለየት ያለ ተለይቶ የተጠቀሰ ተቋም ወይም ቦታ ባይኖርም፣ በአጠቃላይ በእስልምና እና በተለያዩ ወገኖች ላይ ያነጣጠረ ሰፊ የጥላቻ መልዕክት የያዘ ነው።
የሳን ዲዬጎ ፖሊስ አዛዥ ስኮት ዋህል እንደገለጹት፣ ጥቃቱ ከመፈጸሙ ከሁለት ሰዓት በፊት የ17 ዓመቱ ተጠርጣሪ ኬን ክላርክ እናት ለፖሊስ ደውላ ነበር። እናትየው ልጇ፣ መኪናው እንዲሁም በቤት ውስጥ የነበሩ በርካታ መሣሪያዎች መጥፋታቸውን ገልጻ፣ ልጇ ራሱን የማጥፋት ስጋት እንዳለበትና የወታደራዊ መለዮ የለበሰ ሌላ ጓደኛ አብሮት እንዳለ ለፖሊስ ጥቆማ ሰጥታ ነበር። ይህ ጥቆማ ፖሊስን ወደ ከፍተኛ ክትትል ቢያስገባውም፣ ታጣቂዎቹ ግን እኩይ ዓላማቸውን ከመፈጸም አልተገቱም።
ፖሊስ ስፍራው ላይ ሲደርስ የሦስት ሰዎችን አስከሬን ከመስጂዱ ውጪ ያገኘ ሲሆን፣ እስካሁን የሟቾች ስም ይፋ አልተደረገም። ሆኖም ግን ከተገደሉት መካከል አንዱ የመስጂዱ ጥበቃ ሰራተኛ መሆኑ ታውቋል። ፖሊስ የጥበቃ ሰራተኛው ያደረገው ተጋድሎ "ጀግንነት የተሞላበት እና የብዙዎችን ሕይወት የታደገ" ሲል አወድሶታል። ታጣቂዎቹ ሽጉጥ፣ ሾትጋን እና ጠመንጃ ይዘው እንደነበርም ከፖሊስ የራዲዮ መገናኛ ዝርዝሮች ታውቋል።
ማንነቱ የተለየው የ17 ዓመቱ ኬን ክላርክ፣ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱን በኦንላይን የሚከታተል የነጻ ትግል ስፖርት ተጫዋች ነበር። ከ2024 እስከ 2025 ባለው ጊዜ ውስጥ በማዲሰን ከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የትግል ቡድን አባል የነበረ ሲሆን፣ በአንድ ወቅት በውድድር አንደኛ ወጥቶ ሽልማት ጭምር አሸንፎ ነበር። በልጅነቱ (እ.ኤ.አ በ2015) ከፈጸመው የአካል ጥቃት በስተቀር ምንም ዓይነት የዲስፕሊን ጉድለት ታሪክ የሌለው ተማሪ ነበር።
የኬን ክላርክ አያቶች ለሲኤንኤን ሰጡት ቃል፣ በድርጊቱ እጅግ ድንጋጤ ውስጥ መሆናቸውን ገልጸው "በተፈጠረው ነገር በጣም እናዝናለን" ብለዋል። የቀድሞ የትግል ስፖርት ጓደኞቹም ታዳጊው ከተቀረው ቡድን ጋር ለመላመድ እና ጓደኛ ለማፍራት የሚጥር "ጥሩ ልጅ" መስሎ ይታይ እንደነበርና እንዲህ ያለ እስላማዊ ጥላቻ ወይም የዘረኝነት ስሜት ሲያንጸባርቅ ሰምተውት እንደማያውቁ በግርምት ተናግረዋል።
የፌደራል ምርመራ ቢሮ (FBI) ከሳን ዲዬጎ ፖሊስ ጋር በመሆን የተጠርጣሪዎቹን ቤተሰቦች እና ጓደኞች እየመረመረ ሲሆን፣ ከመስጂዱ የደህንነት ካሜራዎች የተገኙ በርካታ ማስረጃዎችን እያጣራ ይገኛል። ፖሊስ አዛዥ ዋህል ሁኔታውን ሲገልጹ፦ "ይህ ለአንድ ነፃ ማህበረሰብ፣ ለከተማችን እና ለህዝባችን ፍጹም አስከፊ ቅዠት ነው" ብለዋል።
20 days ago
የዕለቱ አነጋጋሪ ምስል‼️
ትራምፕ በቤጂንግ የእራት ግብዣ ላይ የቻይናው ፕሬዚዳንት ከመቀመጫቸው ተነስተው ሲሄዱ ትራምፕ የፕሬዝዳንቱን የግል ማስታወሻ ደብተር ሲያገላብጡ መታየታቸው መነጋገሪያ ሆኗል።
seledadotio
seledadotio
ትራምፕ በቤጂንግ የእራት ግብዣ ላይ የቻይናው ፕሬዚዳንት ከመቀመጫቸው ተነስተው ሲሄዱ ትራምፕ የፕሬዝዳንቱን የግል ማስታወሻ ደብተር ሲያገላብጡ መታየታቸው መነጋገሪያ ሆኗል።
seledadotio
seledadotio
20 days ago
በዚህ መንገድ ተነግሯችሁ ፣ተረድታችሁትስ ታውቃላችሁ ?
(መላኩ ብርሃኑ)
ኦቲዝም ሰዎች እንደሚያስቡት ዝም ብሎ "ልዩ" መሆን ብቻ አይደለም! ዝም ብሎ ያልተለመደ "እንግዳ ፀባይ" ማሳየትም ብቻም አይደለም።
አንዳንዴ Autism ከዛም በላይ እጅግ የጠለቀ ነው:: ኦቲዝም ያለባቸው ልጆች ውስጣቸው እጅግ ጩኸት የበዛበት ነው። ያ ጩኸት አቅምን የሚፈታተንና መቼ ምን እንደሚፈጠር የማይታወቅበት፥ ስሜትን የሚያጥለቀልቅ ከባድ ማዕበል ነው።
እኛ በቀላሉ የምናልፋቸው ቀላል ነገሮች ነገሮች ለእነሱ የዕለት ተዕለት አድካሚ የትግል ሜዳዎች ናቸው።
ድምፆች ልክ እንደ አካላዊ ህመም ሲሰሟችሁ አስቡት። ከፍተኛ የቦምብ ፍንዳታ ስትሰሙ ከምትሆኑት ነገር ጋር አነጻጽሩት።
እኛ ቸል የምንለው ‘ቲክ ቲክ’ የሚለው የሰዓት ድምጽ ፥ የመኪና ጡሩምባ፥ ወይም የሰዎች ጫጫታ ለእነሱ ልክ ጆሮ ላይ እንደሚጮህ ስፒከር አእምሮን ሲበጠብጠው ይታያችሁ። እንዲያ ነው የሚሰማቸው። የሚጮኸው የጁስ መፍጫ፣ የሚንጫጩ ሰዎች በነሱ አዕምሮ ውስጥ ሲደርሱ በብዙ መቶ እጥፍ ጨምረው ማብቂያ የሌለው ረብሻ ይፈጥራሉ። ከዚያ ለመሸሽ የሚገቡበት ሲጠፋቸው፣ ጆሯቸውን ሲይዙ ስታዩ በነሱ ቦታ ራሳችሁን ተመልከቱ።
ድምጽ ብቻ አይደለም፣ ብርሃን አይንን አጥበርብረው ህዋሳትን ሲረብሹ አስቡት። እኛ የለመድነው የፀሀይ ብርሃን ወይም የክፍላችን አምፑል አይንን እንደሚያቃጥል ፍም ሲሆንባቸው አስቧቸው። ልክ በጨለማ ቤት ውስጥ ድንገት ሃይለኛ ፓውዛ መብራት ሲለቀቅባችሁ እንደሚሰማችሁ ከባድ ህመም ። 💔
ሀሳቦች ከቃላት በላይ ዐዕምሮ ውስጥ በከፍተኛ ፍጥነት ሲጋልቡ... ጭንቅላት ውስጥ ሺ ሀሳቦች በአንድ ጊዜ ሲጋጩ፥ ነገር ግን አንዱንም አውጥቶ ለመናገር አንደበት ሲታሰር አስቡት።
እናንተ በሰማችሁት መጥፎ ዜና ሳቢያ በከፍተኛ ጭንቀትና ግራ መጋባት ውስጥ ሆናችሁ ሁሉም ነገር ሲዞርባችሁ፣ ማሰብ ሲሳናችሁእንደምትሆኑት ለነርሱ ሁሉም ነገር የሚያልፈው በዚያ ሁኔታ ነው። ያኔ ማምለጥ ይፈልጋሉ፣ እረፍት አልባ ሩጫ፣ ያልተለመደ የሰውነት እንቅስቃሴ፣ ትርጉም አልባ ድምፆች ያወጣሉ። በዚህ የውስጥ ትርምሳቸውን ያረግባሉ።
የሚነኩት ነገር ልስላሴ ወይም ሻካራነት በቆዳቸው በኩል አልፎ ዐምሯቸው ውስጥ ህመም እንደሚፈጥርስ አስባችሁ ታውቃላችሁ? አይጥ የምትፈሩ ሰዎች አይጥ በእጃችሁ ብትነኩ የሚሰማችሁን ስሜት ትገምታላችሁ አይደል? ለነዚህ ልጆች አንዳንድ ነገሮች እንዲዚያ ናቸው፣ ይረብሻሉ።
ዓለም አንድም እንኳን ረጋ የማትል ስትሆን፣ እንደአውሎ ነፋስ ፍጥነት ሁሉም ነገር ውልብልብ ብሎ መያዝ ሲያስቸግር ፣ .. ሁሉም ነገር ወደዐዕምሮ በአንድ ጊዜ ሲመጣ፥ ዐዕምሮ መረጃዎችን አጣርቶ ቦታ ቦታ ለማስያዝ እጅግ ሲጨነቅ አስቡት። 💔
ኦቲዝም ያለባቸው ልጆች ይሄ ሁሉ የውስጥ ጦርነትና የህዋሳት ጫና (Sensory Overload) በውስጣቸው እየተካሄደ ከዚያ ለማምለጥ ሲታገሉ የሚያደርጉትን እንቅስቃሴ፣ የሚሆኑትን ሁኔታ እንደረብሻ እንቆጥረዋለን። ... ምንም እንዳልተፈጠረ "ረጋ በል ! " "ዝም በል !" "ስርዓት ያዝ !" "አታስቸግር !" “አትቁነጥነጥ” ብለን አጭር ትዕዛዝ እንሰጣቸዋለን።
እስኪ ለአንድ ሰከንድ አስቡት... አንድ ኦቲዝም ያለበት ልጅ ይህንን ሁሉ እረፍት የሚያሳጣ ስሜት በውስጥ ተሸክሞ፥ ማዕበሉን ብቻውን እየታገለ፥ ግን ደግሞ ያንን ስሜት የሚገልፅበት ቃል ሲያጣ! … "እባካችሁ ተቸግሬያለሁ፣ ይህ ነገር አልተመቸኝም፣ ተዉኝ! " ማለት ሳይችል ሲቀር!
እንደዚህ ያሉ ልጆችን አብዝቶ መታገስ የሚያስፈልገው ለዚህ ነው! ለእንዲህ አይነት ልጆች ደግነት በጣም ብዙ ትርጉም ያለው ለዚህ ነው! ❤️
ጭንቀታቸውን፣ ያንን ጭንቀት ለማምለጥ የሚያደርጉትን መቅበጥበጥ፣ መሯሯጥ፣ መግቢያ ሲያጡ የሚሆኑትን ነገር መረዳት ብዙ ነገራቸውን ይቀይርላቸዋል !
እኛ የምንሰጣቸው ትንሿ መረዳት፥ ለእነሱ ከሚያስጨንቃቸው ዓለም ለማምለጥ ትልቅ ማረፊያ ትሆናቸዋለች:: ❤️
ምክንያቱም ኦቲዝም እንደ ደም መፍሰስ ወይም እንደ ስብራት ጉዳቱ በአይን በማየት ሊገለጽ አይችልም ። በእነሱ ዘንድ እኛ ከምንገምተው በላይ እጅግ በጣም ጠልቆ የሚሰማ የዕለት ተዕለት የውስጥ ረብሻ አለ ❤️
ኦቲዝም በሽታ አይደለም!
ኦቲዝም ያለባቸው ሰዎች ዓለምን የሚረዱት፣ መረጃን የሚያስተናግዱት እና የሚማሩት ከተለመደው በተለየ (Neurodivergent) መንገድ ነው ።
ሲበሉ፣ ሲጫወቱ፣ ሲፈልጉ በአጠቃላይ አለምን የሚረዱበትም፣ ሚተረጉሙበትም፣ የሚኖሩበትም መንገድ እኛ ከለመድነው የተለየ ነው።
ለመረዳት መሞከርና እነሱን ማገዝ እንጂ ያለልምምድ እና ስልጠና በራሳቸው ተነስተው ወደኛ አለም እንዲመጡ መቆጣት፣ ማመናጨቅ፣ ባስ ሲልም መምታት ተገቢ አይደለም።
የእነሱ የተለየ መሆን የኛን ዓለም ይበልጥ ውብ ያደርጋታል!!
እባካችሁ ኦቲዝም ያለባቸውን ልጆች ከመፍረድ ይልቅ ይበልጥ ጠጋ ብለን ልንረዳቸው እንሞክር ።
ዛሬ ይህንን መልዕክት ማየት፥ መስማት እና መረዳት ያለበት አንድ ሰው ይኖራልና፣ ጽሁፉ ስለ ኦቲዝም ትንሹም ቢሆን ግንዛቤ ከሰጣችሁ Share በማድረግ ለሌሎችም አጋሩ።
(ማስታወሻ! ይህ ጽሁፍ እስካሁን ኦቲዝምን በተመለከተ ከተጻፉት ሁሉ የላቀ ትርጉም የሚሰጥ ሆኖ አግኝቼዋለሁ።ጸሃፊውን ባላውቀውም ኢንተርኔት ላይ አግኝቼው አብራርቼና አሻሽዬ ጽፌዋለሁ። ወደናንተ ደርሶ የኔ ስሜት ተጋብቶባችሁ ከሆነ ተሳክቶልኛል)
(መላኩ ብርሃኑ)
ኦቲዝም ሰዎች እንደሚያስቡት ዝም ብሎ "ልዩ" መሆን ብቻ አይደለም! ዝም ብሎ ያልተለመደ "እንግዳ ፀባይ" ማሳየትም ብቻም አይደለም።
አንዳንዴ Autism ከዛም በላይ እጅግ የጠለቀ ነው:: ኦቲዝም ያለባቸው ልጆች ውስጣቸው እጅግ ጩኸት የበዛበት ነው። ያ ጩኸት አቅምን የሚፈታተንና መቼ ምን እንደሚፈጠር የማይታወቅበት፥ ስሜትን የሚያጥለቀልቅ ከባድ ማዕበል ነው።
እኛ በቀላሉ የምናልፋቸው ቀላል ነገሮች ነገሮች ለእነሱ የዕለት ተዕለት አድካሚ የትግል ሜዳዎች ናቸው።
ድምፆች ልክ እንደ አካላዊ ህመም ሲሰሟችሁ አስቡት። ከፍተኛ የቦምብ ፍንዳታ ስትሰሙ ከምትሆኑት ነገር ጋር አነጻጽሩት።
እኛ ቸል የምንለው ‘ቲክ ቲክ’ የሚለው የሰዓት ድምጽ ፥ የመኪና ጡሩምባ፥ ወይም የሰዎች ጫጫታ ለእነሱ ልክ ጆሮ ላይ እንደሚጮህ ስፒከር አእምሮን ሲበጠብጠው ይታያችሁ። እንዲያ ነው የሚሰማቸው። የሚጮኸው የጁስ መፍጫ፣ የሚንጫጩ ሰዎች በነሱ አዕምሮ ውስጥ ሲደርሱ በብዙ መቶ እጥፍ ጨምረው ማብቂያ የሌለው ረብሻ ይፈጥራሉ። ከዚያ ለመሸሽ የሚገቡበት ሲጠፋቸው፣ ጆሯቸውን ሲይዙ ስታዩ በነሱ ቦታ ራሳችሁን ተመልከቱ።
ድምጽ ብቻ አይደለም፣ ብርሃን አይንን አጥበርብረው ህዋሳትን ሲረብሹ አስቡት። እኛ የለመድነው የፀሀይ ብርሃን ወይም የክፍላችን አምፑል አይንን እንደሚያቃጥል ፍም ሲሆንባቸው አስቧቸው። ልክ በጨለማ ቤት ውስጥ ድንገት ሃይለኛ ፓውዛ መብራት ሲለቀቅባችሁ እንደሚሰማችሁ ከባድ ህመም ። 💔
ሀሳቦች ከቃላት በላይ ዐዕምሮ ውስጥ በከፍተኛ ፍጥነት ሲጋልቡ... ጭንቅላት ውስጥ ሺ ሀሳቦች በአንድ ጊዜ ሲጋጩ፥ ነገር ግን አንዱንም አውጥቶ ለመናገር አንደበት ሲታሰር አስቡት።
እናንተ በሰማችሁት መጥፎ ዜና ሳቢያ በከፍተኛ ጭንቀትና ግራ መጋባት ውስጥ ሆናችሁ ሁሉም ነገር ሲዞርባችሁ፣ ማሰብ ሲሳናችሁእንደምትሆኑት ለነርሱ ሁሉም ነገር የሚያልፈው በዚያ ሁኔታ ነው። ያኔ ማምለጥ ይፈልጋሉ፣ እረፍት አልባ ሩጫ፣ ያልተለመደ የሰውነት እንቅስቃሴ፣ ትርጉም አልባ ድምፆች ያወጣሉ። በዚህ የውስጥ ትርምሳቸውን ያረግባሉ።
የሚነኩት ነገር ልስላሴ ወይም ሻካራነት በቆዳቸው በኩል አልፎ ዐምሯቸው ውስጥ ህመም እንደሚፈጥርስ አስባችሁ ታውቃላችሁ? አይጥ የምትፈሩ ሰዎች አይጥ በእጃችሁ ብትነኩ የሚሰማችሁን ስሜት ትገምታላችሁ አይደል? ለነዚህ ልጆች አንዳንድ ነገሮች እንዲዚያ ናቸው፣ ይረብሻሉ።
ዓለም አንድም እንኳን ረጋ የማትል ስትሆን፣ እንደአውሎ ነፋስ ፍጥነት ሁሉም ነገር ውልብልብ ብሎ መያዝ ሲያስቸግር ፣ .. ሁሉም ነገር ወደዐዕምሮ በአንድ ጊዜ ሲመጣ፥ ዐዕምሮ መረጃዎችን አጣርቶ ቦታ ቦታ ለማስያዝ እጅግ ሲጨነቅ አስቡት። 💔
ኦቲዝም ያለባቸው ልጆች ይሄ ሁሉ የውስጥ ጦርነትና የህዋሳት ጫና (Sensory Overload) በውስጣቸው እየተካሄደ ከዚያ ለማምለጥ ሲታገሉ የሚያደርጉትን እንቅስቃሴ፣ የሚሆኑትን ሁኔታ እንደረብሻ እንቆጥረዋለን። ... ምንም እንዳልተፈጠረ "ረጋ በል ! " "ዝም በል !" "ስርዓት ያዝ !" "አታስቸግር !" “አትቁነጥነጥ” ብለን አጭር ትዕዛዝ እንሰጣቸዋለን።
እስኪ ለአንድ ሰከንድ አስቡት... አንድ ኦቲዝም ያለበት ልጅ ይህንን ሁሉ እረፍት የሚያሳጣ ስሜት በውስጥ ተሸክሞ፥ ማዕበሉን ብቻውን እየታገለ፥ ግን ደግሞ ያንን ስሜት የሚገልፅበት ቃል ሲያጣ! … "እባካችሁ ተቸግሬያለሁ፣ ይህ ነገር አልተመቸኝም፣ ተዉኝ! " ማለት ሳይችል ሲቀር!
እንደዚህ ያሉ ልጆችን አብዝቶ መታገስ የሚያስፈልገው ለዚህ ነው! ለእንዲህ አይነት ልጆች ደግነት በጣም ብዙ ትርጉም ያለው ለዚህ ነው! ❤️
ጭንቀታቸውን፣ ያንን ጭንቀት ለማምለጥ የሚያደርጉትን መቅበጥበጥ፣ መሯሯጥ፣ መግቢያ ሲያጡ የሚሆኑትን ነገር መረዳት ብዙ ነገራቸውን ይቀይርላቸዋል !
እኛ የምንሰጣቸው ትንሿ መረዳት፥ ለእነሱ ከሚያስጨንቃቸው ዓለም ለማምለጥ ትልቅ ማረፊያ ትሆናቸዋለች:: ❤️
ምክንያቱም ኦቲዝም እንደ ደም መፍሰስ ወይም እንደ ስብራት ጉዳቱ በአይን በማየት ሊገለጽ አይችልም ። በእነሱ ዘንድ እኛ ከምንገምተው በላይ እጅግ በጣም ጠልቆ የሚሰማ የዕለት ተዕለት የውስጥ ረብሻ አለ ❤️
ኦቲዝም በሽታ አይደለም!
ኦቲዝም ያለባቸው ሰዎች ዓለምን የሚረዱት፣ መረጃን የሚያስተናግዱት እና የሚማሩት ከተለመደው በተለየ (Neurodivergent) መንገድ ነው ።
ሲበሉ፣ ሲጫወቱ፣ ሲፈልጉ በአጠቃላይ አለምን የሚረዱበትም፣ ሚተረጉሙበትም፣ የሚኖሩበትም መንገድ እኛ ከለመድነው የተለየ ነው።
ለመረዳት መሞከርና እነሱን ማገዝ እንጂ ያለልምምድ እና ስልጠና በራሳቸው ተነስተው ወደኛ አለም እንዲመጡ መቆጣት፣ ማመናጨቅ፣ ባስ ሲልም መምታት ተገቢ አይደለም።
የእነሱ የተለየ መሆን የኛን ዓለም ይበልጥ ውብ ያደርጋታል!!
እባካችሁ ኦቲዝም ያለባቸውን ልጆች ከመፍረድ ይልቅ ይበልጥ ጠጋ ብለን ልንረዳቸው እንሞክር ።
ዛሬ ይህንን መልዕክት ማየት፥ መስማት እና መረዳት ያለበት አንድ ሰው ይኖራልና፣ ጽሁፉ ስለ ኦቲዝም ትንሹም ቢሆን ግንዛቤ ከሰጣችሁ Share በማድረግ ለሌሎችም አጋሩ።
(ማስታወሻ! ይህ ጽሁፍ እስካሁን ኦቲዝምን በተመለከተ ከተጻፉት ሁሉ የላቀ ትርጉም የሚሰጥ ሆኖ አግኝቼዋለሁ።ጸሃፊውን ባላውቀውም ኢንተርኔት ላይ አግኝቼው አብራርቼና አሻሽዬ ጽፌዋለሁ። ወደናንተ ደርሶ የኔ ስሜት ተጋብቶባችሁ ከሆነ ተሳክቶልኛል)
Sponsored by
Surafel
21 days ago
የኢትዮጵያ አየር መንገድ የኤር ትርዒት ለጎብኚዎች ክፍት ሆነ
የአፍሪካ ኩራት የሆነው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ 80ኛ ዓመት የምሥረታ በዓሉን ምክንያት በማድረግ ያዘጋጀው ልዩ የማይንቀሳቀስ የኤር ትርዒት (Static Air Show) ዛሬ በቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በድምቀት ተከፍቷል።
አየር መንገዱ ባለፉት ሰማንያ ዓመታት በጽናት ተጉዞ ለደረሰበት ዓለም አቀፋዊ ስኬት ማስታወሻ ይሆን ዘንድ በተከፈተው በዚህ ዝግጅት ላይ፣ ታሪካዊና ዘመናዊ አውሮፕላኖች ለዕይታ ቀርበዋል።
ይህ ልዩ ትርዒት የአየር መንገዱን ጥንካሬና የደረሰበትን የላቀ የአቪዬሽን ቴክኖሎጂ አቅም ለጎብኚዎች በቅርበት የሚያሳይ ድንቅ አጋጣሚ ሆኖ ተገኝቷል።
ይህ በዓይነቱ ለየት ያለ ዝግጅት የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከአነስተኛ አጀማመር ተነስቶ እንዴት የዓለም ተመራጭ መሆን እንደቻለ ትውልድ ትምህርት እንዲቀስምበት ታስቦ የተዘጋጀ ነው።
ጎብኚዎች የአየር መንገዱን ታሪካዊ ጉዞ የሚያሳዩ ልዩ ኩነቶችን ከመመልከታቸውም በላይ፣ የደንበኞቹ የልብ አድራሽ የሆነውን የዚህን ታላቅ ተቋም የ80 ዓመታት የድል ጉዞ በጋራ እያከበሩ ይገኛሉ።
seledadotio
seledadotio
የአፍሪካ ኩራት የሆነው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ 80ኛ ዓመት የምሥረታ በዓሉን ምክንያት በማድረግ ያዘጋጀው ልዩ የማይንቀሳቀስ የኤር ትርዒት (Static Air Show) ዛሬ በቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በድምቀት ተከፍቷል።
አየር መንገዱ ባለፉት ሰማንያ ዓመታት በጽናት ተጉዞ ለደረሰበት ዓለም አቀፋዊ ስኬት ማስታወሻ ይሆን ዘንድ በተከፈተው በዚህ ዝግጅት ላይ፣ ታሪካዊና ዘመናዊ አውሮፕላኖች ለዕይታ ቀርበዋል።
ይህ ልዩ ትርዒት የአየር መንገዱን ጥንካሬና የደረሰበትን የላቀ የአቪዬሽን ቴክኖሎጂ አቅም ለጎብኚዎች በቅርበት የሚያሳይ ድንቅ አጋጣሚ ሆኖ ተገኝቷል።
ይህ በዓይነቱ ለየት ያለ ዝግጅት የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከአነስተኛ አጀማመር ተነስቶ እንዴት የዓለም ተመራጭ መሆን እንደቻለ ትውልድ ትምህርት እንዲቀስምበት ታስቦ የተዘጋጀ ነው።
ጎብኚዎች የአየር መንገዱን ታሪካዊ ጉዞ የሚያሳዩ ልዩ ኩነቶችን ከመመልከታቸውም በላይ፣ የደንበኞቹ የልብ አድራሽ የሆነውን የዚህን ታላቅ ተቋም የ80 ዓመታት የድል ጉዞ በጋራ እያከበሩ ይገኛሉ።
seledadotio
seledadotio
23 days ago
40 ደፈንኩ
#fastmereja I ፖለቲከኛና አክቲቪስት ጀዋር መሐመድ 40ኛ ዓመት የልደት በዓላቸውን ባከበሩበት ዕለት፣ በህይወት ዘመናቸው ስላሳለፉት የትግል ጉዞ የሚዳስስ የግል መልዕክት አስተላልፈዋል።
ጀዋር መሐመድ በዛሬው ዕለት ባሰፈሩት ማስታወሻ፣ ገና በለጋ የልጅነት ዕድሜያቸው በኤሌመንተሪ ትምህርት ቤት ተማሪዎችን በማስተባበር የመጀመሪያውን የተቃውሞ ሰልፍ ካደረጉ 25 ዓመታት ማለፋቸውን አስታውሰዋል። ፖለቲከኛው ይህንን የቆየ የትግል ታሪካቸውን "አገዛዞችን የመጋፈጥ አባዜ" ሲሉ የገለጹት ሲሆን፣ ይህም ስሜት አብሮአቸው የተወለደ እንደሚመስላቸው ገልጸዋል።
በተለይም ጭቆና፣ ብዝበዛ እና መድሎ "አለርጂ" እንደሆኑባቸው የጠቀሱት ጀዋር፣ እነዚህን ድርጊቶች በተመለከቱ ቁጥር ወደ አክቲቪዝም ስራቸው እንደሚመለሱና ይህም ባህሪ እስከ ህይወት ፍጻሜያቸው ድረስ አብሮአቸው እንደሚቆይ ያላቸውን እምነት አጋርተዋል። እድሜያቸው ገፍቶ ጸጉራቸው ቢሸብትም፣ የፍትህ መጓደልን የመቃወም ፍላጎታቸው እንዳልቀነሰም አመልክተዋል።
በመጨረሻም፣ ለልደት በዓላቸው የእንኳን አደረሰህ መልዕክት ያስተላለፉላቸውን ደጋፊዎቻቸውንና ወገኖቻቸውን አመስግነዋል።
#fastmereja I ፖለቲከኛና አክቲቪስት ጀዋር መሐመድ 40ኛ ዓመት የልደት በዓላቸውን ባከበሩበት ዕለት፣ በህይወት ዘመናቸው ስላሳለፉት የትግል ጉዞ የሚዳስስ የግል መልዕክት አስተላልፈዋል።
ጀዋር መሐመድ በዛሬው ዕለት ባሰፈሩት ማስታወሻ፣ ገና በለጋ የልጅነት ዕድሜያቸው በኤሌመንተሪ ትምህርት ቤት ተማሪዎችን በማስተባበር የመጀመሪያውን የተቃውሞ ሰልፍ ካደረጉ 25 ዓመታት ማለፋቸውን አስታውሰዋል። ፖለቲከኛው ይህንን የቆየ የትግል ታሪካቸውን "አገዛዞችን የመጋፈጥ አባዜ" ሲሉ የገለጹት ሲሆን፣ ይህም ስሜት አብሮአቸው የተወለደ እንደሚመስላቸው ገልጸዋል።
በተለይም ጭቆና፣ ብዝበዛ እና መድሎ "አለርጂ" እንደሆኑባቸው የጠቀሱት ጀዋር፣ እነዚህን ድርጊቶች በተመለከቱ ቁጥር ወደ አክቲቪዝም ስራቸው እንደሚመለሱና ይህም ባህሪ እስከ ህይወት ፍጻሜያቸው ድረስ አብሮአቸው እንደሚቆይ ያላቸውን እምነት አጋርተዋል። እድሜያቸው ገፍቶ ጸጉራቸው ቢሸብትም፣ የፍትህ መጓደልን የመቃወም ፍላጎታቸው እንዳልቀነሰም አመልክተዋል።
በመጨረሻም፣ ለልደት በዓላቸው የእንኳን አደረሰህ መልዕክት ያስተላለፉላቸውን ደጋፊዎቻቸውንና ወገኖቻቸውን አመስግነዋል።
24 days ago
ሃላባ ከተማ ወደ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ በማደግ አዲስ ታሪክ ጻፈ
#ethiopia | በኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ ምድብ ለ ውስጥ ተፎካካሪ የነበረው ሃላባ ከተማ ደሴ ከተማን 1 ለ 0 በሆነ ውጤት በመርታት ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መግባቱን አረጋግጧል።
በሐዋሳ ከተማ በተደረገው በዚህ ወሳኝ ፍልሚያ እስራኤል ሸጎሌ ያስቆጠራት ብቸኛ ግብ ክለቡ የውድድር ዘመኑ ሊጠናቀቅ አንድ ጨዋታ እየቀረው የታላቁን ሊግ ተቀላቃይነት እንዲያረጋግጥ አስችላለች።
ቡድኑ ይህንን ታሪካዊ ድል በማስመዝገቡ በከተማው ደማቅ አቀባበል የተደረገለት ሲሆን የከተማው አስተዳደርም ለተጫዋቾችና ለአሰልጣኝ ቡድን አባላት የቤት መስሪያ ቦታና የገንዘብ ሽልማት አበርክቷል።
ከዚህ በተጨማሪም ክለቡን ለማበረታታት ሲጓዙ ህይወታቸውን ላጡና ጉዳት ለደረሰባቸው ደጋፊዎች ቤተሰቦች የገንዘብና የማስታወሻ ድጋፍ ተደርጓል።
ሃላባ ከተማ የከፍተኛ ሊጉ አጠቃላይ አሸናፊ መሆን የቻለው ጋሞ ጨንቻን በመለያ ምት በማሸነፍ ነው።
ለዘመናት የቆየው የፕሪሚየር ሊግ የመቀላቀል ህልም እውን በሆነበት በዚህ ወቅት በዋና አሰልጣኝ በሺር አብደላ የሚመራው የቴክኒክ ቡድንና ተጫዋቾች በህዝብ ዘንድ ከፍተኛ አድናቆት እየተቸራቸው ይገኛል።
የሃላባ ዓለም አቀፍ ስታዲየም አገልግሎት መስጠት በጀመረበት ማግስት የተገኘው ይህ ውጤት ለከተማው ህዝብ ልዩ ትርጉም ያለው ሲሆን ደጋፊዎችም ለክለቡ ስኬት ላሳዩት ጽናት ምስጋና ቀርቧል።
#halabakenema #ethiopiapremierleague #ethiopianfootball #halabacity #footballnews #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | በኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ ምድብ ለ ውስጥ ተፎካካሪ የነበረው ሃላባ ከተማ ደሴ ከተማን 1 ለ 0 በሆነ ውጤት በመርታት ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መግባቱን አረጋግጧል።
በሐዋሳ ከተማ በተደረገው በዚህ ወሳኝ ፍልሚያ እስራኤል ሸጎሌ ያስቆጠራት ብቸኛ ግብ ክለቡ የውድድር ዘመኑ ሊጠናቀቅ አንድ ጨዋታ እየቀረው የታላቁን ሊግ ተቀላቃይነት እንዲያረጋግጥ አስችላለች።
ቡድኑ ይህንን ታሪካዊ ድል በማስመዝገቡ በከተማው ደማቅ አቀባበል የተደረገለት ሲሆን የከተማው አስተዳደርም ለተጫዋቾችና ለአሰልጣኝ ቡድን አባላት የቤት መስሪያ ቦታና የገንዘብ ሽልማት አበርክቷል።
ከዚህ በተጨማሪም ክለቡን ለማበረታታት ሲጓዙ ህይወታቸውን ላጡና ጉዳት ለደረሰባቸው ደጋፊዎች ቤተሰቦች የገንዘብና የማስታወሻ ድጋፍ ተደርጓል።
ሃላባ ከተማ የከፍተኛ ሊጉ አጠቃላይ አሸናፊ መሆን የቻለው ጋሞ ጨንቻን በመለያ ምት በማሸነፍ ነው።
ለዘመናት የቆየው የፕሪሚየር ሊግ የመቀላቀል ህልም እውን በሆነበት በዚህ ወቅት በዋና አሰልጣኝ በሺር አብደላ የሚመራው የቴክኒክ ቡድንና ተጫዋቾች በህዝብ ዘንድ ከፍተኛ አድናቆት እየተቸራቸው ይገኛል።
የሃላባ ዓለም አቀፍ ስታዲየም አገልግሎት መስጠት በጀመረበት ማግስት የተገኘው ይህ ውጤት ለከተማው ህዝብ ልዩ ትርጉም ያለው ሲሆን ደጋፊዎችም ለክለቡ ስኬት ላሳዩት ጽናት ምስጋና ቀርቧል።
#halabakenema #ethiopiapremierleague #ethiopianfootball #halabacity #footballnews #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
25 days ago
ለሀላባ ከተማ ተጫዋቾች ሽልማት ተበረከተ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 2፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የሀላባ ከተማ አስተዳደር የኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ አሸናፊ ለሆነው የሀላባ ከተማ ተጫዋቾች የገንዘብ እና የቤት መስሪያ ቦታ ሽልማት አበርክቷል፡፡
የ2018 የኢትዮጵያ ከፍተኛ አጠቃላይ የዋንጫ አሸናፊ የሆነው ሀላባ ከተማ ክለብ ወደ ሀላባ ከተማ ሲገባ ደማቅ አቀባበል ተደርጎለታል።
ክለቡ ወደ 2019 የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ እንዲቀላቀል ላደረጉ የአሰልጣኝ ቡድን አባላት እና ተጫዋቾች የቤት መስሪያ ቦታ እና የገንዘብ ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።
ከዚህ በፊት ክለቡን ለመደገፍ ሲጓዙ ሕይወታቸውን ላጡ እና ጉዳት ለደረሰባቸው ደጋፊዎች እና ቤተሰቦቻቸው የማስታወሻ እና የገንዘብ ድጋፍ ተደርጓል።
በሽልማት ሥነ ሥርዓቱ የሀላባ ቁሊቶ ከተማ ከንቲባ፣ የክለቡ ፕሬዚዳንት ገመዳ መሃመድ፣ የሀላባ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ሙዲን ሁሴን እና ሌሎች ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች እና የክለቡ ደጋፊዎች ተገኝተዋል።
ሀላባ ከተማ ጋሞ ጨንቻን በመለያ ምቶች 4 ለ 3 በማሸነፍ የ2018 የኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ አጠቃላይ አሸናፊ መሆኑ ይታወሳል።
በእንዳልካቸው ወዳጄ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 2፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የሀላባ ከተማ አስተዳደር የኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ አሸናፊ ለሆነው የሀላባ ከተማ ተጫዋቾች የገንዘብ እና የቤት መስሪያ ቦታ ሽልማት አበርክቷል፡፡
የ2018 የኢትዮጵያ ከፍተኛ አጠቃላይ የዋንጫ አሸናፊ የሆነው ሀላባ ከተማ ክለብ ወደ ሀላባ ከተማ ሲገባ ደማቅ አቀባበል ተደርጎለታል።
ክለቡ ወደ 2019 የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ እንዲቀላቀል ላደረጉ የአሰልጣኝ ቡድን አባላት እና ተጫዋቾች የቤት መስሪያ ቦታ እና የገንዘብ ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።
ከዚህ በፊት ክለቡን ለመደገፍ ሲጓዙ ሕይወታቸውን ላጡ እና ጉዳት ለደረሰባቸው ደጋፊዎች እና ቤተሰቦቻቸው የማስታወሻ እና የገንዘብ ድጋፍ ተደርጓል።
በሽልማት ሥነ ሥርዓቱ የሀላባ ቁሊቶ ከተማ ከንቲባ፣ የክለቡ ፕሬዚዳንት ገመዳ መሃመድ፣ የሀላባ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ሙዲን ሁሴን እና ሌሎች ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች እና የክለቡ ደጋፊዎች ተገኝተዋል።
ሀላባ ከተማ ጋሞ ጨንቻን በመለያ ምቶች 4 ለ 3 በማሸነፍ የ2018 የኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ አጠቃላይ አሸናፊ መሆኑ ይታወሳል።
በእንዳልካቸው ወዳጄ
26 days ago
"የኔ ዜማ" ምሽት!
አንጋፋ የኪነጥበብ ምሽት!
እባክዎ ሸር በማድረግ ተባበሩን!
55ኛው የባህል ማዕከል የኪነጥበብ ምሽት ረቡዕ ግንቦት 05፥2018 ዓ.ም ይካሄዳል።
በዕለቱም አንዱ ኮከብ፤ ተወዳጁ ድምጻዊ ዳዊት ፅጌ የክብር እንግዳችን ሆኖ በመካከላችን በመገኘት ሙያዊ ልምዱን ያካፍለናል።
እንዲሁም ግጥሞች ፣ ወግ ፣ ሙዚቃና ሞኖሎግ ለእናንተ ውድ ታዳሚዎቻችንን በባህል ማዕከል አዳራሽ ከቀኑ በ 11: 30 ጀምሮ ተሰናድቶ ይጠብቃችኃል።
#ማስታወሻ :— ፕሮግራሙ ላይ ለመታደም የምትፈልጉ በአሁን ሰዓት የዩኒቨርስቲው ተማሪ ያልሆናችሁ የስነ-ጽሑፍ አፍቃሪያን መግቢያው በ5ተኛ በር በኩል ነው።
አንጋፋ የኪነጥበብ ምሽት!
እባክዎ ሸር በማድረግ ተባበሩን!
55ኛው የባህል ማዕከል የኪነጥበብ ምሽት ረቡዕ ግንቦት 05፥2018 ዓ.ም ይካሄዳል።
በዕለቱም አንዱ ኮከብ፤ ተወዳጁ ድምጻዊ ዳዊት ፅጌ የክብር እንግዳችን ሆኖ በመካከላችን በመገኘት ሙያዊ ልምዱን ያካፍለናል።
እንዲሁም ግጥሞች ፣ ወግ ፣ ሙዚቃና ሞኖሎግ ለእናንተ ውድ ታዳሚዎቻችንን በባህል ማዕከል አዳራሽ ከቀኑ በ 11: 30 ጀምሮ ተሰናድቶ ይጠብቃችኃል።
#ማስታወሻ :— ፕሮግራሙ ላይ ለመታደም የምትፈልጉ በአሁን ሰዓት የዩኒቨርስቲው ተማሪ ያልሆናችሁ የስነ-ጽሑፍ አፍቃሪያን መግቢያው በ5ተኛ በር በኩል ነው።
29 days ago
ሚያዝያ 27! ለአምስት ዓመታት በጨለማ የተዋጠው የኢትዮጵያ ሰማይ በነፃነት ጎህ የፈካበት፣ የግፍ ወረራ ቀንበር የተሰበረበት ታላቅ ዕለት ነው።
ነገር ግን የአባቶቻችን ገድል ለእኛ የታሪክ ማስታወሻ ብቻ ነው? ወይስ ዛሬን የምንመራበት ኮምፓስ?
በዚህ ቪዲዮ የአባቶቻችንን የዱር በገደል ተጋድሎ ከዛሬው የልማትና የቴክኖሎጂ አርበኝነት ጋር እናነፃፅራለን።
#ethiopianpatriotsday #arbenyoch #victoryday #grandethiopianrenaissancedam #gerd
Sponsored by
Surafel
1 month ago
የሙዚቃ አርበኛው ጥላሁን ገሠሠ……
------------------------
ታላቁ የሙዚቃ ሰው ለግማሽ ምዕተ ዓመት በዘለቀው የሙያ ሕይወቱ ያልዳሰሳቸው ርዕሠ ጉዳዮች የሉትም፡፡
ማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ሁነቶች ሁሉ አልቀሩትም፡፡
አርቲስቱ በረዥሙ የድምፃዊነት ሕይወቱ ዘመን የተጫወታቸውን ዘፈኖች ትክክለኛ ቁጥር ደፍሮ መናገር የሚችል ሰው የለም።
ከባንዶች ጋር አልያም በመድረክ የተጫወታቸው ነገር ግን የመቀረጽ ዕድል ያላገኙ ብዙ ዘፈኖች ሊኖሩ እንደሚችሉ ይታመናል።
ቀድሞም በልጅነቱ አንጎራጓሪ የነበረው ታላቁ የሙዚቃ ሰው፣ የድምጻዊነት ሕይወቱን በይፋ የጀመረው 1947 ሀገር ፍቅር ማኅበር ሲቀጠር ነው፡፡
በሀገር ፍቅር ማኅበር የሁለት ዓመት ተኩል አካባቢ ቆይታው፣ ጥላ ከለላዬ፣ ጽጌረዳ ነሽ፣ ደጉ ንጉሥ እና ፍቅሬ ሰውነቴ የተሰኙ ዘፈኖችን ለህዝብ አቅርቦ ተወዳጅነትን አትርፎ ነበር።
በክብር ዘበኛ ኦርኬስትራ አባልነት ከተቀጠረ በኋላ ከ1950ዎቹ የመጀመሪያ ዓመታት ጀምሮ እስከ 1960ዎቹ አጋማሽ ድረስ በክብር ዘበኛ ኦርኬስትራ አጃቢነት ተጫውቷል።
በመቀጠልም ከክብር ዘበኛ ኦርኬስትራ ወደ አንደኛ ክፍለ ጦር ወይም የማዕከላዊ ዕዝ የሙዚቃ ባንድ ተቀላቅሎ የባንዱ ኮከብ ድምጻዊ ሆኖ እስከ 1970ዎቹ መጨረሻ ድረስ ቆይቷል።
#በምድር ጦር ኦርኬስትራ ፡-ጩኸቴን ብትሰሙ፣ እኔ ነኝ ወይ አንቺ፣ አይከዳሽም ልቤ እና ማስታወሻ፣
#በፖሊስ ኦርኬስትራ፡- ሰው ማንን ይመስላል እና ስማ ፣
#በሬይንቦው ባንድ፡- በይ ደህና ክረሚ እና ስንብት ፣
#በኤግዚቢሽን ባንድ፡- የኔ ፍላጎቴ እና በደህና እስኪገጥመን ፣
#በሙላቱ አስታጥቄ ባንድ፡- ኩሉን ማን ኳለሽ፣ አለኝታዬ፣ ላንቺ ብዬ፣ ስትሄድ ስከተላት፣ ትዝ አለኝ የጥንቱ እና የሀገሬ ሽታን ፣
#ከአይቤክስ ባንድ ጋር፡- ውበትሽ ይደነቃል፣ ጽጌረዳ፣ አካም ነጉማ፣ የቆለኛ ልጅ፣ ፍቅሬ ሆይ ያላንቺ እና ሌሎች አምሥት ዘፈኖች የሚገኙበትን ካሴት ሰርቷል፡፡
#ሮሃ ባንድ ፡- በ1980 የ13 ወር ፀጋ እና በ1984 ደግሞ እንቆቅልሽ የተሰኙትን ካሴቶችን የሰራ ሲሆን፣ በ1981 ጥላሁን፣ ብዙነሽ፣ ማህሙድ እና ሒሩት በጋራ ያወጡት ካሴትም በሮሃ ባንድ የታጀበ ነው።
#በዋሊያስ ባንድ፡- ከሌለህ የለህም እና ይቺ ናት ጨዋታ አልበሞች የታጀቡት ደግሞ በዋሊያስ ባንድ ነው።
ጥላሁን ሀገር ወዳድነትን የሚያጎሉ በርካታ ዘፈኖችን ተጫውቷል። ከተጫወታቸው ሀገራዊ ዘፈኖች ውስጥም በ1969 የተጫወተው "አጥንቴም ይከስከስ" እንዲሁም በ1979 በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ስቱዲዮ ተቀርፆ ለሕዝብ የቀረበው "ቃል ኪዳን" የተሰኘው ዘፈን ለየት ብለው ይታወሳሉ። "ቃል ኪዳን" ባሕር ማዶ የሚኖሩ ወገኖች ወደ ሀገር ቤት እንዲመለሱ በጥላሁን ጥበባዊ አንደበት የቀረበ "የእናት ሀገር ጥሪ" ነበር ማለት ይቻላል።
በሀገር ፍቅር ማኅበር "ጥላ ከለላዬ ኢትዮጵያ ሀገሬ"ን በመጫወት በይፋ የተጀመረው የጥላሁን የግማሽ ምዕተ ዓመት የሙዚቃ ሕይወት "ቆሜ ልመርቅሽ" በሚሰኘውና ሕይወቱ ከማለፉ በፊት ባስቀረፀው የመጨረሻው አልበም ነው የተደመደመው።
ጥላሁን በጥበብ ሕይወቱ ስለ ኢትዮጵያ ሲቀኝና ሲዘምር ኖሯል፡፡ ልዩ የሀገር እና የሕዝብ ፍቅርንም አስተምሮናልም፡፡
በድምፁ ሐውልቱን ሲቀርጽ የኖረው ታላቅ ከያኒ ዛሬ በአዲስ አበባ የተሰራለት ሐውልት በይፋ ተመርቋል፡፡
ታላቁን የጥበብ ሰው ፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን ከቤተሰብ እና ከወዳጆቹ ጋር በመሆን በየአመቱ መስከረም ላይ በትንፋሼ ኮንሰርት እንደሚዘክረው ይታወቃል፡፡
------------------------
ታላቁ የሙዚቃ ሰው ለግማሽ ምዕተ ዓመት በዘለቀው የሙያ ሕይወቱ ያልዳሰሳቸው ርዕሠ ጉዳዮች የሉትም፡፡
ማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ሁነቶች ሁሉ አልቀሩትም፡፡
አርቲስቱ በረዥሙ የድምፃዊነት ሕይወቱ ዘመን የተጫወታቸውን ዘፈኖች ትክክለኛ ቁጥር ደፍሮ መናገር የሚችል ሰው የለም።
ከባንዶች ጋር አልያም በመድረክ የተጫወታቸው ነገር ግን የመቀረጽ ዕድል ያላገኙ ብዙ ዘፈኖች ሊኖሩ እንደሚችሉ ይታመናል።
ቀድሞም በልጅነቱ አንጎራጓሪ የነበረው ታላቁ የሙዚቃ ሰው፣ የድምጻዊነት ሕይወቱን በይፋ የጀመረው 1947 ሀገር ፍቅር ማኅበር ሲቀጠር ነው፡፡
በሀገር ፍቅር ማኅበር የሁለት ዓመት ተኩል አካባቢ ቆይታው፣ ጥላ ከለላዬ፣ ጽጌረዳ ነሽ፣ ደጉ ንጉሥ እና ፍቅሬ ሰውነቴ የተሰኙ ዘፈኖችን ለህዝብ አቅርቦ ተወዳጅነትን አትርፎ ነበር።
በክብር ዘበኛ ኦርኬስትራ አባልነት ከተቀጠረ በኋላ ከ1950ዎቹ የመጀመሪያ ዓመታት ጀምሮ እስከ 1960ዎቹ አጋማሽ ድረስ በክብር ዘበኛ ኦርኬስትራ አጃቢነት ተጫውቷል።
በመቀጠልም ከክብር ዘበኛ ኦርኬስትራ ወደ አንደኛ ክፍለ ጦር ወይም የማዕከላዊ ዕዝ የሙዚቃ ባንድ ተቀላቅሎ የባንዱ ኮከብ ድምጻዊ ሆኖ እስከ 1970ዎቹ መጨረሻ ድረስ ቆይቷል።
#በምድር ጦር ኦርኬስትራ ፡-ጩኸቴን ብትሰሙ፣ እኔ ነኝ ወይ አንቺ፣ አይከዳሽም ልቤ እና ማስታወሻ፣
#በፖሊስ ኦርኬስትራ፡- ሰው ማንን ይመስላል እና ስማ ፣
#በሬይንቦው ባንድ፡- በይ ደህና ክረሚ እና ስንብት ፣
#በኤግዚቢሽን ባንድ፡- የኔ ፍላጎቴ እና በደህና እስኪገጥመን ፣
#በሙላቱ አስታጥቄ ባንድ፡- ኩሉን ማን ኳለሽ፣ አለኝታዬ፣ ላንቺ ብዬ፣ ስትሄድ ስከተላት፣ ትዝ አለኝ የጥንቱ እና የሀገሬ ሽታን ፣
#ከአይቤክስ ባንድ ጋር፡- ውበትሽ ይደነቃል፣ ጽጌረዳ፣ አካም ነጉማ፣ የቆለኛ ልጅ፣ ፍቅሬ ሆይ ያላንቺ እና ሌሎች አምሥት ዘፈኖች የሚገኙበትን ካሴት ሰርቷል፡፡
#ሮሃ ባንድ ፡- በ1980 የ13 ወር ፀጋ እና በ1984 ደግሞ እንቆቅልሽ የተሰኙትን ካሴቶችን የሰራ ሲሆን፣ በ1981 ጥላሁን፣ ብዙነሽ፣ ማህሙድ እና ሒሩት በጋራ ያወጡት ካሴትም በሮሃ ባንድ የታጀበ ነው።
#በዋሊያስ ባንድ፡- ከሌለህ የለህም እና ይቺ ናት ጨዋታ አልበሞች የታጀቡት ደግሞ በዋሊያስ ባንድ ነው።
ጥላሁን ሀገር ወዳድነትን የሚያጎሉ በርካታ ዘፈኖችን ተጫውቷል። ከተጫወታቸው ሀገራዊ ዘፈኖች ውስጥም በ1969 የተጫወተው "አጥንቴም ይከስከስ" እንዲሁም በ1979 በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ስቱዲዮ ተቀርፆ ለሕዝብ የቀረበው "ቃል ኪዳን" የተሰኘው ዘፈን ለየት ብለው ይታወሳሉ። "ቃል ኪዳን" ባሕር ማዶ የሚኖሩ ወገኖች ወደ ሀገር ቤት እንዲመለሱ በጥላሁን ጥበባዊ አንደበት የቀረበ "የእናት ሀገር ጥሪ" ነበር ማለት ይቻላል።
በሀገር ፍቅር ማኅበር "ጥላ ከለላዬ ኢትዮጵያ ሀገሬ"ን በመጫወት በይፋ የተጀመረው የጥላሁን የግማሽ ምዕተ ዓመት የሙዚቃ ሕይወት "ቆሜ ልመርቅሽ" በሚሰኘውና ሕይወቱ ከማለፉ በፊት ባስቀረፀው የመጨረሻው አልበም ነው የተደመደመው።
ጥላሁን በጥበብ ሕይወቱ ስለ ኢትዮጵያ ሲቀኝና ሲዘምር ኖሯል፡፡ ልዩ የሀገር እና የሕዝብ ፍቅርንም አስተምሮናልም፡፡
በድምፁ ሐውልቱን ሲቀርጽ የኖረው ታላቅ ከያኒ ዛሬ በአዲስ አበባ የተሰራለት ሐውልት በይፋ ተመርቋል፡፡
ታላቁን የጥበብ ሰው ፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን ከቤተሰብ እና ከወዳጆቹ ጋር በመሆን በየአመቱ መስከረም ላይ በትንፋሼ ኮንሰርት እንደሚዘክረው ይታወቃል፡፡
1 month ago
ሚያዝያ 27 የታሪክ ማኅደር ተገልጦ የሚነበብበት የትላንት ትዝታ ብቻ አይደለም - የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት
***********************
ሚያዝያ 27 ለእኛ የታሪክ ማኅደር ተገልጦ የሚነበብበት የትላንት ትዝታ ብቻ አይደለም፤ የአርበኞች አባቶቻችንን እና እናቶቻችንን የድል መንፈስ እንደ ብዕር በመጠቀም አዲስ የታሪክ ምዕራፍ መጻፍ የጀመርንበት የትንሣኤ ጉዟችን መነሻ መሠረት ነው! ሚያዝያ 27 የነፃነት ማስታወሻ ብቻ ሳይሆን፣ ወጣቱ ትውልድ ሀገሩን በክብር ለመረከብ ላቡን የሚያፈስበትና ያለውን የሚሰጥበት የቁርጠኝነት ቀን ነው!
ከ85 ዓመታት በፊት አባቶቻችን በደምና በአጥንታቸው ሀገርን ጠብቀው የማቆየት ታሪካዊ ግዴታቸውን በድል ተወጥተዋል። ዛሬ የታሪኩ ምዕራፍ ተቀይሮ ተረኝነቱ የእኛ ሆኗል፤ እነርሱ በነፃነት ያቆዩልንን ሀገር እኛ በዕውቀታችን፣ በላባችንና በሥራችን የመገንባት የዘመኑ አርበኝነት አደራ አለብን።
አባቶች በጠመንጃ ሀገር ጠበቁ፤ እኛ በቴክኖሎጂ ሀገር እንገነባለን። አባቶች ዳር ድንበር አስከበሩ፤ እኛ ድህነትን አሸንፈን ብልጽግናን እናረጋግጣለን። አባቶች ለነፃነት ወደቁ፤ እኛ ለታላቅነት እንቆማለን። ይህ የትውልድ ቅብብል ነው ። ያለ አባቶች ጥበቃ ዛሬ የምንገነባት ሀገር ባልኖረች ነበር፤ ያለ እኛ ግንባታም አባቶች የጠበቋት ሀገር ትርጉም ያለው ሕይወት ለዜጎቿ መስጠት አትችልም። በመሆኑም ትናንት በጀግንነት የተረከብናትን ሀገር፣ ዛሬ በሥልጣኔ አንጸን ለቀጣዩ ትውልድ የማስረከብ የሞራል ዕዳ፣ የሀገር አደራ አለብን።
ለዚህም ነው ኢትዮጵያዊያን ከስንዴ ልመና ለመላቀቅ ወገባችንን አጥብቀን፣ ማረሻችንን ጨብጠን የተነሳነው፣ ለዚህ ነው አለም እኪደመም ተደምረን 48 ቢሊዮን ችግኝ የተከለነወ፣ ለዚህ ነው ከመቀነታችን ፈትተን፣ ከጉርሳችን ቀንሰን ህዳሴያችንን እውን ያደረግነው፣ ለዚህ ነው የዘመናት የጉስቁልና ምልክት የነበሩ ያረጁ ከተሞቻችንን ለመለወጥ እያመመን የበረታነው፣ ለዚህ ነው የከረሙ ስብራቶቻችንን ለመጠገን እንመካከር ያለነው፣ ለዚህ ነው ዙሪያው ተቸንክሮብን እስከመቼ እንኖራለን ያልነው! ለዚህ ነው የታዳሽ ሀይል መሠረት ለመጣል እየተጋን ያለነው ፣ ለዚህ ነው የአፍሪካ ትልቁን የአቬሽን ማዕከል እየገነባን ያለነው አደራ ስላለብን፣ ሀገርን በላብ የማሻገር አደራ!
በመሆኑም በዚህ ታሪካዊ ቀን፣ እያንዳንዱ ዜጋ በተሰማራበት የሥራ መስክ ሁሉ ለሀገሩ ጡብ የሚደረድር የራሱ ዘመን አርበኛ መሆን ይጠበቅበታል። ዛሬ እኛ የምናከናውናቸው የልማት ሥራዎች፣ የምናሳየው ጽኑ አንድነትና ዳር የምናደርሳቸው ግዙፍ ሀገራዊ ፕሮጀክቶች ሀገርን ጠብቀው ላቆዩን አባቶች የምንሰጠው ትልቁ የክብር መግለጫና የታሪክ ምላሻችን ነው።"
ክብር ሀገርን ጠብቀው ላቆዩን አባቶች!
በትጋት ሀገርን ለሚገነቡ ልጆች!
ኢትዮጵያ በላባችን ታላቅ ትሆናለች!
Ethiopian Broadcasting Corporation #ኢትዮጵያ #ድል #
***********************
ሚያዝያ 27 ለእኛ የታሪክ ማኅደር ተገልጦ የሚነበብበት የትላንት ትዝታ ብቻ አይደለም፤ የአርበኞች አባቶቻችንን እና እናቶቻችንን የድል መንፈስ እንደ ብዕር በመጠቀም አዲስ የታሪክ ምዕራፍ መጻፍ የጀመርንበት የትንሣኤ ጉዟችን መነሻ መሠረት ነው! ሚያዝያ 27 የነፃነት ማስታወሻ ብቻ ሳይሆን፣ ወጣቱ ትውልድ ሀገሩን በክብር ለመረከብ ላቡን የሚያፈስበትና ያለውን የሚሰጥበት የቁርጠኝነት ቀን ነው!
ከ85 ዓመታት በፊት አባቶቻችን በደምና በአጥንታቸው ሀገርን ጠብቀው የማቆየት ታሪካዊ ግዴታቸውን በድል ተወጥተዋል። ዛሬ የታሪኩ ምዕራፍ ተቀይሮ ተረኝነቱ የእኛ ሆኗል፤ እነርሱ በነፃነት ያቆዩልንን ሀገር እኛ በዕውቀታችን፣ በላባችንና በሥራችን የመገንባት የዘመኑ አርበኝነት አደራ አለብን።
አባቶች በጠመንጃ ሀገር ጠበቁ፤ እኛ በቴክኖሎጂ ሀገር እንገነባለን። አባቶች ዳር ድንበር አስከበሩ፤ እኛ ድህነትን አሸንፈን ብልጽግናን እናረጋግጣለን። አባቶች ለነፃነት ወደቁ፤ እኛ ለታላቅነት እንቆማለን። ይህ የትውልድ ቅብብል ነው ። ያለ አባቶች ጥበቃ ዛሬ የምንገነባት ሀገር ባልኖረች ነበር፤ ያለ እኛ ግንባታም አባቶች የጠበቋት ሀገር ትርጉም ያለው ሕይወት ለዜጎቿ መስጠት አትችልም። በመሆኑም ትናንት በጀግንነት የተረከብናትን ሀገር፣ ዛሬ በሥልጣኔ አንጸን ለቀጣዩ ትውልድ የማስረከብ የሞራል ዕዳ፣ የሀገር አደራ አለብን።
ለዚህም ነው ኢትዮጵያዊያን ከስንዴ ልመና ለመላቀቅ ወገባችንን አጥብቀን፣ ማረሻችንን ጨብጠን የተነሳነው፣ ለዚህ ነው አለም እኪደመም ተደምረን 48 ቢሊዮን ችግኝ የተከለነወ፣ ለዚህ ነው ከመቀነታችን ፈትተን፣ ከጉርሳችን ቀንሰን ህዳሴያችንን እውን ያደረግነው፣ ለዚህ ነው የዘመናት የጉስቁልና ምልክት የነበሩ ያረጁ ከተሞቻችንን ለመለወጥ እያመመን የበረታነው፣ ለዚህ ነው የከረሙ ስብራቶቻችንን ለመጠገን እንመካከር ያለነው፣ ለዚህ ነው ዙሪያው ተቸንክሮብን እስከመቼ እንኖራለን ያልነው! ለዚህ ነው የታዳሽ ሀይል መሠረት ለመጣል እየተጋን ያለነው ፣ ለዚህ ነው የአፍሪካ ትልቁን የአቬሽን ማዕከል እየገነባን ያለነው አደራ ስላለብን፣ ሀገርን በላብ የማሻገር አደራ!
በመሆኑም በዚህ ታሪካዊ ቀን፣ እያንዳንዱ ዜጋ በተሰማራበት የሥራ መስክ ሁሉ ለሀገሩ ጡብ የሚደረድር የራሱ ዘመን አርበኛ መሆን ይጠበቅበታል። ዛሬ እኛ የምናከናውናቸው የልማት ሥራዎች፣ የምናሳየው ጽኑ አንድነትና ዳር የምናደርሳቸው ግዙፍ ሀገራዊ ፕሮጀክቶች ሀገርን ጠብቀው ላቆዩን አባቶች የምንሰጠው ትልቁ የክብር መግለጫና የታሪክ ምላሻችን ነው።"
ክብር ሀገርን ጠብቀው ላቆዩን አባቶች!
በትጋት ሀገርን ለሚገነቡ ልጆች!
ኢትዮጵያ በላባችን ታላቅ ትሆናለች!
Ethiopian Broadcasting Corporation #ኢትዮጵያ #ድል #
1 month ago
"በኢትዮጵያ ሰማይ ላይ
የሚበራው የሙዚቃ ኮከብ "
ከአለባቸው ደሳለኝ አበሻ (ለንደን)
#ethiopia | "ድምፁ የሀገር ሰንደቅ ዓላማ ያህል ክብር የሚሰጠው ጥላሁን ገሰሰ ለግማሽ ክፍለ ዘመን ያህል በኢትዮጵያ ሙዚቃ ውስጥ በነበረው ከፍተኛ አስተዋፅኦ የኢትዮጵያ ሙዚቃ ንጉሥ በሚል መጠሪያ ይታወቃል።
ለዚህ የጥበብ ሰው እንዲህ ያለ ጥልቅ እና ልብ የሚነካ ትዝታ ማዘጋጄት የሚቻለው የጥላሁን ገሰሰን ስራዎችን ብቻ ሳይሆን የእርሱን የውስጥ ማንነት ሠብዕናን ለጥበብ የነበረውን ፍቅር በሚገባ የተረዳ መሆን አለበት ።
ወይንም ደግሞ
የዚህን ታላቅ ምትሐተኛ ድምፃዊ የጥበብ ልክና የድምፅ ብቃት በአግባቡ ለመረዳት የእርሱን ግለ ታሪክ ብቻ ሳይሆን የኢትዮጵያን ዘመናዊ ሙዚቃ ታሪክና የጥላሁን ገሰሰን ሰፊ የሥራ ክምችቶች በጥልቀት መመርመር የግድ ይላል።
ምክኒያቱም
ጥላሁን ገሰሰ ማለት የኢትዮጵያ የ50 ዓመታት የደስታ የሐዘን የድልና የሽንፈት ታሪክ በድምፅ የተቀረጸበት "ሕያው ማህደር" ነው።
ጥላሁን ገሰሰ ድምፁን እንደፈለገ የማዘዝ Vocal Control ልዩ ተሰጥኦ ነበረው።
በጣም ረጅምና ከፍተኛ ድምፅ በሚጠይቁ High notes እንዲሁም በጣም ረጋ ያሉና ዝቅተኛ ድምፅ በሚሹ Low notes ዜማዎች ላይ እኩል ብቃት ነበረው።
የትንፋሽ ቁጥጥሩ ረጅም ስንኞችን ሳያቋርጥና ትንፋሽ ሳይጠረው የመጨረስ ችሎታው የሚደነቅ ነበር።
የጥላሁንን ስራዎች ስንመረምር በአንድ የሙዚቃ ዘውግ ብቻ ያልተገደበ መሆኑን እንረዳለን
ባህላዊና ዘመናዊ የባህል ሙዚቃዎችን ከዘመናዊ መሣሪያዎች ኦርኬስትራ ጋር አዋህዶ በማቅረብ ረገድ ቀዳሚ ነበር።
በጥላሁን ገሠሠ ድምፅ ያልተዘፈነ የሕይወት ክፍል የለም ማለት ይቻላል ።
ከጥልቅ የፍቅር ስሜት እስከ ሃገር ፍቅር ከማህበራዊ ትችት እስከ መንፈሳዊ መዝሙራት ድረስ የተፃፉ ግጥሞችና ዜማዎች የጥላሁንን ገሠሠን ድምፅ ለማድመቅ ሳይሆን ለመፈተን ጭምር የተዘጋጁ ይመስሉ ነበር።
በህይወት በቆየባቸው ሦስት የተለያዩ ሥርዓቶች በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ በደርግና በኢህአዴግ ውስጥ አልፏል። በእነዚህ ሁሉ ጊዜያት የሕዝብ ተወዳጅነቱን ጠብቆ መቆየቱ የሙዚቃ ሥራዎቹ ከፖለቲካዊ ለውጦች በላይ የሕዝብን የልብ ትርታ የሚነኩ መሆናቸውን ያሳያል።
ባጭሩ ጥላሁን ገሰሰ ለኢትዮጵያ ሙዚቃ ያለው አስተዋጽኦ ልክ እንደ አንድ ትልቅ "ኢንሳይክሎፒዲያ" ነው። አንዱን ገጽ አንብቦ ስለ መጽሐፉ ሙሉ ግንዛቤ ማግኘት እንደማይቻል ሁሉ
አንዱን ዘፈን አዳምጦ ስለ ጥላሁን ገሰሰ ማወቅ አይቻልም ።
እያንዳንዱ ዘፈኑ የራሱ የሆነ የቴክኒክ የታሪክና የስሜት ጥልቀት አለው።
ስለዚህ የጥላሁንን ታላቅነት ለመረዳት የኢትዮጵያን የሙዚቃ ጉዞ አብሮ መመርመር የግድ ነው ያልኩት ወድጄ አይደለም ።
ዘፈኖቹን ሲዘፍን በቃላት ብቻ ሳይሆን በፊቱ መግለጫና በሰውነት እንቅስቃሴው Body Language ጭምር ስሜቱን ለታዳሚው ያጋባ ነበር።
በተለይ የሐዘን ዜማዎችን ሲዘፍን አብሮ የሚያለቅስ የደስታ ሲሆን ደግሞ አብሮ ፈገግ የሚል ድምፃዊ ተዋና ጭምር ነበረ በዘፈኖቹ ውስጥ ሰውን ማክበርን ስራን መውደድንና አንድነትን ይሰብካል። ዘፈኑ የሰውን ልጅ ክብርና ማንነት የሚተነትን ድንቅ ስራ የሚሰራ ምትሀተኛ ድምፃዊ ነበር ።
ጥላሁን ገሰሰ በአንድ ወቅት በመድረክ ላይ እያለ በደረሰበት የጉሮሮ ህመም ምክንያት ለተወሰነ ጊዜ ድምፁ ተዘግቶ ነበር። ያን ጊዜ መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ተጨንቆና ፀልዮ ድምፁ ሲመለስለት ያደረገው የመጀመሪያ ኮንሰርት በዚያን ወቅት በኢትዮጵያ የሙዚቃ ታሪክ ውስጥ ከፍተኛውን የሰው ቁጥር ያስመዘገበ ነበር ። ይህ የሚያሳየው ሕዝቡ ለጥላሁን ያለው ፍቅር ከአንድ ድምፃዊ በላይ እንደ ቤተሰብ አባል የሚያየው መሆኑን ነው።
ስለ ፍቅር ብቻ ሳይሆን ስለ ሰው ልጅ ሕይወት ባዶነት የሚተርክ ጥልቅ ፍልስፍና ነበረው ።
ታዋቂው የኢትዮጵያ የሙዚቃ ንጉሥ ክቡር ዶክተር ጥላሁን ገሰሰ መስከረም 17 ቀን 1933 ዓ.ም አዲስ አበባ ውስጥ ተወልዶ ያደገው ግን በወሊሶ ከተማ ነው ።
ጥላሁን በ1950ዎቹ መጀመሪያ ላይ ወደ አዲስ አበባ በመምጣት መጀመሪያ ሐገር ፍቅር ቲያትርን በኋላም ዝነኛውን የክብር ዘበኛ የሙዚቃ ቡድንን ተቀላቅሎ ከዕንስት ፍቅር እስከ አገር ፍቅር ከባህላዊ እስከ ዘመናዊ ሙዚቃ በድምፃዊነት ከ400 በላይ ዘፈኖችን ተጫውቶ ልዩ ብቃቱን አስመስክሯል ።
ጥላሁን
ለኢትዮጵያ ሙዚቃ ላበረከተው ወደር የለሽ አስተዋጽኦ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የክብር ዶክትሬት ዲግሪ ተሰጥቶታል። ጥላሁን ገሠሠ ከዚህ ዓለም በሞት የተለየው
በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር ሚያዝያ 11 ቀን 2001 ዓ.ም. የፋሲካ እለት ሲሆን በድንገተኛ የልብ ህመም ምክንያት አርፎ በቅድስት ሥላሴ ካቴድራል የቀብር ሥነሥርዓቱ ተፈጽሟል።
የክቡር ዶክተር ጥላሁን ገሰሰ ማረፍ መላውን የኢትዮጵያ ሕዝብና የጥበብ አፍቃሪወችን በከፍተኛ ድንጋጤና ሃዘን ውስጥ ጥሎ የነበረ ክስተት ነው። በወቅቱ በጋዜጦች በሬዲዮና በቴሌቪዥን የተላለፉት መልዕክቶች ጥላሁን ለሀገሩ ያለውን ትልቅ ቦታ የሚያንፀባርቁ ነበሩ።
በአዲስ አበባ ከተማ የነበሩ የታክሲ አሽከርካሪዎች ሐዘን ፈፅሞ የማይረሳ ነበረ ።
ለጥላሁን ገሰሰ ክብር ሲሉ ለቀናት ጥቁር ጨርቅ በታክሲዎቻቸው ላይ አስረውና የእርሱን ሙዚቃ ብቻ ከፍተው በማጫወት ሃዘናቸውን ገልፀውለታል።
የጥላሁን ገሰሰ ሞት በሀገር ውስጥ ብቻ ሳይሆን በዓለም አቀፍ ደረጃም ትኩረት አግኝቶ ነበር።
ታዋቂው ደራሲ ሎሬት ጸጋዬ ገብረመድህንም
እንዲህ አሉ ።
"ጥላሁን የኢትዮጵያ ሕዝብ የጋራ ድምፅ ነው። እርሱ ሲዘፍን መላው ኢትዮጵያዊ ራሱን ያዳምጣል።"
ድምፃዊ ማህሙድ አህመድ"ጥላሁን ለእኛ ለድምፃውያን መምህራችን ብቻ ሳይሆን የሙዚቃው ዓምድ ነበር። ጥላሁን ሞተ ማለት የኢትዮጵያ ሙዚቃ ግማሽ አካሉን አጣ ማለት ነው።" ሲል ቁጭቱን ገልፀዋል ።
በቀብር ሥነ ሥርዓቱ ላይ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ አዲስ አበባውያን ወደ አደባባይ በመውጣት "ንጉሥ አይሞትም" እያሉ ሲያለቅሱ እንደነበር በታሪክ ተመዝግቧል።
ይህም አንድ ድምፃዊ በሀገር ደረጃ ያለውን ክብርና ተሰሚነት ያሳየ ትልቅ ክስተት ነበር።
አንድ የልብ አድናቂው የሆነ ሠው በማህበራዊ ሚዲያ እንዲህ ብሎ ፅፎት አንብቢያለሁ ።
" በእርግጥም ጥላሁን በድምፁ ተአምር የመስራት አቅም ነበረው። ድምፁ ተስፋ የቆረጠውን የሚያፅናና የታመመውን የሚፈውስና የራቀውን የሚያቀራርብ
ስለነበረ ድምፁ ተቀርፆ ስለቀረ ቢሞትም ስንናፍቀው እናገኘዋለን ስናዝን እናለቅስበታለን ሀገራችን ስትጠራ በእሱ ድምፅ አቤት ብለን ለአንድነቷ እንቆማለን" በማለት ጥላሁንን ገልፆት ነበር ።
ሌላው የቅርብ ጓደኛው የጥበብ ሰው ደበበ እሸቱ ነው
"ጥላሁን በሕይወት ዘመኑ ሁሉ ለሀገሩ የዘመረ በችግር ጊዜ ደግሞ ድምፁን ለድሆች የሰጠ
ታላቅ ሰው ነው።
የሞተው በስጋ ቢሆንም በዜማው ቅላፄና በግጥም ስንኞች ውስጥ "ዘላለማዊ" ሆኖ ተተክሏል።
እንዲህ ያለ ድምፅ ዓለማችን በአንድ ዘመን አንዴ ብቻ የምትለግሰን ስጦታ ነው "
ሲል ምስክርነቱን ገልጿል።
በእርግጥም ጥላሁን የዘመናዊ ሙዚቃችን "ፊደል" እና "መዝገበ ቃላት" ሆኖ አልፏል። ከድምፅ ጥራት በላይ የዜማ አጣጣልና ስሜትን የመግለጽ ጥበቡ ማንም የማይደረስበት ከፍታ ላይ ስለነበር በአንድ አባባል ብቻ ጥላሁንን መግለፅ አይቻልም።
እሱ ባለብዙ ምዕራፍና ተነቦ የማይጠገብ ባለ ብዙ ገጽ ድርሳን ነው !
ጥላሁን ለሙያው ብቻ ሳይሆን ለሰው ልጅ የነበረው ሰብአዊ ክብርም ድንቅ ነበር። ረሀብ ሲመጣ በዜማው የሚማፀን ሀገር ስትቸገር አጥንቴም ይከስከስ ብሎ የሚቆም እና ለሰው ልጅ ፍቅር ቅድሚያ የሚሰጥ የጥበብ ሰው ነው ። ባጭሩ ጥላሁን ገሠሠ ማለት ለኢትዮጵያውያን የድምፅ ብቻ ሳይሆን የህሊና ምስክር ነው።
ዛሬም ድረስ ስሙ ሲነሳ አብሮ የሚነሳው ክብሩ ትህትናውና
ያ የማይደገም ማንነቱ ነው።
ጥላሁን ገሠሠን የመሠለ ታላቅ ሰው የኢትዮጵያ ዘመናዊ ሙዚቃን የአዋለደ ብለን ብንገልፀው ተገቢ ይመስለኛል ከጥላሁን ገሠሠ ስራዎች መካከል ይህማ ተአምር ነው የሚያሰኜኘኝ ሁልጊዜ ብሰማቸው አዲስ የሚሆኑብኝ ብዙ ዘፈኖች ቢኖሩትም "እዩት ስትናፍቀኝ ከአጠገቤ እያለች" የሚለው ስንኝ ሲነሳ ግን የጥላሁንን ድምፅና ያንን የሚመስጥ አዘፋፈኑን አብሮ የመስማት ያህል ይመስጠኛል እዩት ስትናፍቀኝ ከአጠገቤ እያለች
እንዲህ ያለው መውደድ ለወሬም አይመች ! የሚለው ግጥም የፍቅርን ረቂቅነትና የማይመረመር ባህሪ በአጭር ቃላት የገለጸበት ድንቅ ስራው ነው።
ጥላሁን ለዚህ ዘፈን የሰጠው እረዥም ትንፋሽና በመድረክ ላይ ቆሞ የአይን አስተያየቱ የልዩ ተሰጥኦው መገለጫዎቹ ናቸው።
የሠው ልጅ ናፍቆት ብዙውን ጊዜ ትዝታው የሚመጣው ሰው ሲርቅ ነው። ነገር ግን ጥላሁን አጠገቤ እያለች ናፈቀችኝ ማለቱ ፍቅር ከስጋዊ መገኘት በላይ የሆነ የነፍስ ጥማት መሆኑን ስጋ አልብሶ አሳይቶናል ።
ይህ ለወሬ የማይመች ቃላት የማይገልፁት ጥልቅ ስሜት ነው ። ይህንንም በዚያ ረጅም ትንፋሽ ነፍስን በሚያከነፍ ድምፁ ሲያዜመው እውነቱን በውስጣችን ውስጥ እናገኘዋለን።
ጥላሁን ሲዘፍን ትንፋሹን የሚጠቀምበት መንገድ እና ስሜቱን በድምፅ ቀለም የመቀየር ችሎታው ምትሐተኛ ያሰኘዋል። ያንን የናፍቆት ጣጣ በገዛ ራሱ ላይ አድርጎ ሲያዜመው አድማጩ የራሱ ህመም አድርጎ እንዲቀበለው የማድረግ ልዩ ኃይል ነበረው።
ጥላሁን ገሠሠ በስጋ ቢለየንም በኢትዮጵያውያን ልብ ውስጥ ግን አሁንም ንጉሥ ነው።
ትውልድ ያልፋል ጥላሁን ግን ይኖራል።
ሙዚቃ ይቀየራል የጥላሁን ስራዎች ግን ሁልጊዜ አዲስ ናቸው።
ሰላም ሲጠፋ ጥላሁን ፍቅር ይላል ሀገር ስትናፈቅ ጥላሁን ሀገሬ ይላል።
ጥላሁን ገሠሠ በድምፁ ብቻ ሳይሆን ለፍቅር በሰጠው ክብርን በገለፀበት ጥበብ የኢትዮጵያ የዘላለም የፍቅር አምባሳደር ነው።
እንዲህ ያለው የጥበብ ሰው የፍቅርን ኃያልነት በእሱ ስራዎች ውስጥ ስንመለከት በእርግጥም ፍቅር ስሜት ብቻ አይደለም የሚለውን ሃሳብ በጥላሁን ዜማዎች ውስጥ ሙሉ ማረጋገጫውን እናገኛለን ጥላሁን ገሠሠ የፍቅርን ሌላኛውን ገጽታ ቁርጠኝነትንና ክብርን ያሳየበት ድንቅ ስራው ነው። ከላይ እንደገለፅኩት ፍቅር ራስን አሳልፎ መስጠት ነው
እዚህ ዘፈን ላይ ደግሞ ፍቅር ሁለትዮሽ መረዳዳት መሆኑን ይነግረናል።
ቻልኩት ፍቅር ለብቻዬ !!
ይህ አገላለጽ በጣም የሚቆረቁር ነው። ፍቅር እንደ አንድ ሸክም ሆኖ አንደኛው ወገን ብቻውን ሲሸከመው የሚሰማውን ድካም ያሳያል። "ለብቻዬ መሸከም ሰልችቶኛል" የሚል የልብ ጩኸት አለበት። ፍቅር የሁለት ሰው ቅኝት እንጂ የአንድ ሰው ብቸኛ ትግል መሆን እንደሌለበት ያስገነዝበናል።
ስለ ፍቅር አልገባሽም
እዚህ ጋር ጥላሁን ፍቅር ማለት ዝም ብሎ አብሮ መሆን ሳይሆን ጥልቅ የሆነ
ሚስጥር ወይም ትርጉም እንዳለው ይገልጻል። ግዴለሽነት እና ችላ ማለት ፍቅርን የሚገድሉ መርዞች መሆናቸውን በምሬት ይናገራል።
አትምጪ ይቅር ሲል ደግሞ የክብር ውሳኔውን ያሳውቃል ።
ፍቅር ስሜት ብቻ አለመሆኑን ያረጋግጣል። አንድ ሰው በጥልቅ እያፈቀረ ግን ክብሩ ሲነካ ወይም ምላሽ ሲያጣ ይቅር ብሎ የመወሰን አቅም ሊኖረው እንደሚገባ ያሳያል።
ፍቅር መስዋዕትነት ቢሆንም ዋጋ በማይሰጠው ቦታ ላይ ግን ራስን ማዳንና ይቅር ማለትም የፍቅር አካል ነው። የሚገርመው ደግሞ ጥላሁን ይህነን ዘፈን ሲዘፍነው በቁጣና በቁጭት ሳይሆን በጥልቅ ሀዘንና በከበረ ስሜት ነው። ያንን አትምጪ ይቅር የሚለውን ቃል ሲያወጣው ውስጡ እየፈለጋት ግን መከባበር የሌለበት ፍቅር እንደማይፀና አውቆ በቁርጠኝነት ሲናገረው ይታየናል።
ከላይ እንዳነሳሁት አትምጪ ይቅር የሚለው ስንኝ የቁርጠኝነትና የክብር ገጹ ሲሆን ሌላው ደግሞ የፍቅርን ንፁህ መስዋዕትነትና ትህትና የሚያሳይ ድንቅ ምዕራፍ ነው።
እነዚህ ስንኞች ውስጥ የምናያቸው የጥላሁን ድርሳናት
እኔ ልሁን እንጂ የማልጠቅም እርካሽ ! የሚለው አገላለፅ በፍቅር ውስጥ ያለን ፍጹም ትህትና ያሳያል። ራሱን ዝቅ አድርጎ የሚወዳትን ሰው ግን ከፍ ያደርጋታል። ይህ እኔነት ጠፍቶ አንቺነት የነገሰበት የፍቅር ጫፍ ነው።
ከህይወቴ አብልጨ ሲል
ራስን አሳልፎ የመስጠት
ፍልስፍና በተግባር የሚያሳይ ታአምር ነው። ለሰው ልጅ ከህይወቱ በላይ ምንም የለውም ነገር ግን ፍቅር ያንን ውድ ህይወት እንኳ ከአንቺ አያበልጠውም ብሎ እንዲያምን ያደርገዋል።
ፍቅር ለሰላምና ለደስታ ብቻ ሳይሆን ለችግርና ለፈተናም ዝግጁ መሆኑን ይነግረናል።
መከራና ስቃይ ይቆየኝ ግዴለኝም
የሚወደው ሰው ደህንነትና ሰላም እስካለ ድረስ እሱ በራሱ ላይ ለሚመጣው መከራ ግድ የለውም። ይህ ነው እንግዲህ ፍቅርን ተአምር የሚያሰኘው እግዜር በጥበቡ ከአንቺ ብቻ አይለየኝ የሚለው ቃል ፍቅር በሰው ጥረት ብቻ ሳይሆን በመለኮታዊ ጥበብና ፈቃድ የሚፀና መሆኑን የሚያሳይ የልብ ፆሎት በመሆኑ መንፈሳዊ ልመና ይጨምርበታል ።
ታዲያ የዚህን ድምፃዊ ተአምራዊ ተቃርኖዎችን ስንመለከት
ጥላሁንን ልዩ የሚያደርገው በአንድ በኩል አትምጪ ይቅር ብሎ በክብር የመወሰን አቅም በሌላ በኩል ደግሞ ከህይወቴ አብልጨ እወድሻለሁ ብሎ ራስን የመስጠት ርህራሄ አብሮት መኖሩ ነው።
እነዚህ ሁለት ተቃራኒ የሚመስሉ ግን ጥልቅ የሆኑ የፍቅር ገጾች ናቸው።
ጥላሁን እነዚህን ሁሉ ስሜቶች በድምፅ ቀለም እየቀያየረ ሲያቀርባቸው ድምፁ ብቻ ሳይሆን ነፍሱ አብራ የምትዘፍን ይመስላል።
እንዲህ ያለውን ከህይወት በላይ የመውደድ ስሜት በዚህ ዘመን በብዛት እናገኘዋለን ብሎ ማሰብ የዋህነት ነው። ምክኒያቱም
የጥላሁንን ጥበብ ከመዝፈን ባለፈ ወደ መፍጠር ደረጃ ከፍ ያደርገዋል።
ለምን ቢባል ጥላሁን ገሠሠ ዜማንና ግጥምን ሲያዋህድ የሚፈጠረው ነገር ተራ ሙዚቃ አይደለም ይልቁንም ያልተጠኑ ምስጢራዊ ተሰጥኦዎች ያሉበት ይመስላል
ብዙ አድናቂወቹ እንደ ሚስማሙበት ጥላሁን ገሠሠ ሲዘፍን ፍቅር ረቂቅ ሃሳብ መሆኑ ቀርቶ የሚዳሰስ የሚታይና የሚሰማ አካል ይኖረዋል።
ቃላቶቹ ከአፉ ሲወጡ ሕይወት ይዘራሉ ያፈቀረው ሰው ቁስሉ ይታየናል የናፈቀው ሰው ትንፋሹ ይሰማናል። ይህ ደግሞ በቴክኒክ ብቻ የሚመጣ ሳይሆን ከነፍስ የሚመነጭ ምትሃት በመሆኑ ፍቅር እንደ ሰው ቆሞ እንዲሄድ የማድረግ ጥልቅና ረቂቅ
ጥበብ ያለው ድምፃዊ መሆኑ ነው ።
ብዙዎቻችን ውስጣችን ያለውን ጥልቅ ፍቅር በቃላት መግለፅ ያቅተናል። ጥላሁን ግን ያንን መግለፅ ያቃተንን ስሜት ሰርቆ ወስዶ በዜማ አቅልጦ ወርቅ አርጎ መልሶ ለእኛው ይሰጠናል።
እኔንም እንዲህ ነው የሚሰማኝ! እንድንል ያደርገናል። ይህ ተሰጥኦው ነው ፍቅርን ስጋ ለብሶ ቆሞ እንዲሄድ የሚያደርገው።
ሌላው የጥላሁን ገሰሰ ድምፅ ሁለንተናዊ ድምፅ መሆኑ ነው። እድሜ ጾታ ወይም የትምህርት ደረጃ አይወስነውም። ህፃኑም አዋቂውም የተማረውም ያልተማረውም በዜማው ውስጥ የራሳቸውን ታሪክ ያገኛሉ።
ይህ ደግሞ ጥላሁን የሰው ልጅን የጋራ የፍቅር ህመም ጠንቅቆ እንደሚያውቅ ማሳያ ነው።
የጥላሁን ድምፅ በሳይንስ አልተጠናም እንጂ በውስጡ ትልቅ የፍቅር ላብራቶሪ ነበረው ማለት ይቻላል።
ግጥሙን ይቀበላል ጥሬ እቃ !
በድምፅ ቀለሙ ያዋህደዋል ሂደት !
በመጨረሻም ሕያው ፍቅርን ለዓለም ያበረክታል ውጤት !! በዚህ ምክኒያት
ጥላሁን ገሠሠ ሞቶም በሰዎች ልብ ውስጥ እንዲነግስ አድርጎታል :: ምክንያቱም የፈጠራቸው የፍቅር አካላት ዛሬም በየቤታችን በየመኪናችንና በየልባችን ውስጥ ቆመው እየሄዱ ነው።
ይህ የእውነት ተአምረኛ ተሰጥኦው ነው። ዛሬ ባለው ዘመናዊ የሙዚቃ ኢንዱስትሪ ውስጥ እንዲህ ያለውን መንፈሳዊ ጥልቅነት ማግኘት እጅግ ብርቅ ሆኗል። ከእንስት ፍቅር ወጥተን ጥላሁንን ወደ ሐገር ፍቅር ስንመነዝረው የቆመበት ከፍታው ላይ እስከ አሁን ማንም ....ማንም አልደረሠበት ። በዚህ አጋጣሚ
በህይወቴ ዘመኔ በአይኔ ያየሁትን ምስክርነት ባቀርበው ደስ ይለኛል ጥለሁን ገሠሠ ከታሪክ መዝገብ በላይ የሆነ የአንድን ሕዝብ ማንነትና ወኔ የቀሰቀሰ የመንፈስ ተአምር ነው የምነግራችሁ ።
ጊዜው 1974 አስመራ የቀይ ኮኮብ ዘመቻ አሉላ አባ ነጋ አዳራሽ ውስጥ ይመስለኛል ።
ጥላሁን ገሠሠ ጋሻና ጎራዴ ይዞ የአርበኛ ልብስ ለብሶ አጥንቴም ይከስከስ ደሜም ይፍሠስላት
ግን ሐገሬን ጭራሽ አይደፍራትም ጠላት
እያለ መድረኩን ሞልቶት ብቅ ሲል ከባለስልጣን እሰከ ተራው ተመልካች ከመቀመጫው ተነስቶ በመቆም በማያቋርጥ ጩህትና ጭብጨባ ያጅቡታል ።
ጥላሁን ገሠሠ በዚያ ቅጽበት የዘፈነውን ብቻ ሳይሆን የኖረውንና የታሪካችንን ድምፅ ሆኖ ተመለከትኩት ።
ጥላሁን በህዝብ ጭብጨባና ጬህት ታጅቦ መድረኩ ላይ ሲንጎራደድ አዳራሹ ድብልቅልቁ ወጣ ።
ያን... ምህታታት የተሞላበት ትርኢት ስመለከት
የአድዋ ጀግኖች መቃብር ከፍተው የተነሱ ይመስል ነበር።
ማለቴ ጥላሁን በድምፁ ብቻ ሳይሆን በቆይታው ጊዜን የማቆም ወይም ታሪክን የመቀስቀስ ኃይል እንደነበረው የመመልከት ዕድል አግኝቻለሁ ።
ጥላሁንን በዚያች ቅፅበት
በሕይወት እያለ ሐውልቱን አቁሞ አዳራሹ ውስጥ ታሪኩን ፅፎት ወጣ ።
በእርግጥ ሐውልት የማይናገርና የማይሰማ የድንጋይ ምስል ነው ጥላሁን ግን በሕይወት ያለ የሚተነፍስ የሚዘፍንና የሚራመድ የኢትዮጵያዊነት ሐውልት ነበር።
ዛሬም ቢሆን ስራዎቹ ያንን ግርማ ሞገስና ያንን ሐውልታዊ ፅናት እያስታወሱኝ እስከእለተ ሞቴ ድረስ ልረሳው አልችልም እንዲህ አይነት ድርጊት
ፍቅር ስሜት ብቻ አይደለም ራስን አሳልፎ መስጠት ነው በጥላሁን ገሰሰ የሀገር ፍቅር ዜማዎች ውስጥ ኢትዮጵያን ደጋግመን እናያታለን
አጥንቴም ይከስከስ ደሜም ይፍሰስላት የሚለው ቃል ዛሬም ድረስ ፍፁም ....ፍፁም መስዋዕትነት ነው።
ሀገሩን እንደ ሚወዳት እናት ወይም ሚስት አድርጎ ለሷ ክብር መሞትን እንደ ትልቅ ፀጋ መቁጠር ከፍ ያለ የፍቅር ደረጃ መግለጫ ነው።
ተመልካቹ በሙሉ ሳይቀመጥ ከሁለት ጊዜ በላይ ይደገም እያለ መጠየቁ ጥላሁን ድምፃዊ ብቻ ሳይሆን መሪ መሆኑን በአንድ ዜማ ሕዝብን የማስተሳሰር በአንድ ወኔ በጋራ የማቆም ተአምራዊ አቅሙን አረጋግጨበታለሁ ።
በዚያች ቅፅብት ቲያትር ቤቱ በጩሄትና በጭብጨባ ቀውጢ ሲሆን ጥላሁን ገሠሠ በድምፁ ብቻ የጠላትን ምሽግ የሚያፈርስ ጀግና መስሎ ነበር የሚታየው ።
ምንም እንኳን ዛሬ በሞት ቢለየንም ያ አስመራ ላይ የተመለከትኩት የሐገር ፍቅር ስሜት ሐውልት ሆኖ በልቤ ውስጥ ተቀርፆ ቆሟል።
ጥላሁን ገሰሰን ልዩ የሚደርገው ሌላው መገለጫው
ለፍቅር ሲዘፍን የፍቅር ሐውልት
ለሀገር ሲዘፍን የጀግንነት ሐውልት
ለሰው ልጅ ክብር ሲዘፍን የሰብአዊነት ሐውልት ነው!
ለዚህ ስኬት ደግሞ ከጥላሁን ድምፅ ጀርባ የነበሩት የወርቃማው ዘመን ታላላቅ የጥበብ ሰዎች ገጣሚያንና የዜማ አቀናባሪዎች ሚና ከፍተኛ እንደነበር ምስክሩ ታሪክና ሕዝቡ ነው።
ጥላሁን ገሰሰ ግጥምና ዜማን
ከነጄነራል አማኑኤል አብርሃም
ሻምበል አፈወርቅ ዮሐንስ
ነጋሽ ገብረማርያም
ተስፋዬ አበበ አየለ ማሞ ሳህሌ ደጋጎ ክፍሌ አቦቸር ከመሳሰሉት የክብር ዘበኛ እና የፖሊስ ኦርኬስትራዎች
ተቀብሎ ሲያንቆረቁረው ሙዚቃው ከድምፅ አልፎ የሚዳሰስ ሕያው መንፈስ የመሆን አቅም ነበረው።
ዛሬ ላይ ሆኜ ያንን ትርኢት ሳስታውሰው ጥላሁን ለኢትዮጵያ ሙዚቃና ለኢትዮጵያዊነት ያለው ትርጉም ምን ያህል ጥልቅ ስሜት እንደሆነ አሁን ድረስ እንደ ህልም ይታየኛል ።
ያኔ መድረክ ላይ ሲወጣ የነበረው ግርማ ሞገስና ድምፁ ሲስተጋባ የተሰማኝ ስሜት ዛሬም ድረስ ዘፈኑን ስሰማው "የጦር ፊታውራሪ" የነበረ ጀግና ያህል ትዝ ይለኛል !!
ጥላሁን በመድረክ ላይ የነበረውን የበላይነት እና የሕዝብን ስሜት የመምራት ብቃቱን በሚገባ የመግለፅ አቅም ነበረው ።
ጥላሁን ዝም ብሎ ድምፃዊ ሳይሆን በዜማው የታጠቀ የሀገር መከታ ወታደርም ሆኖ እንደነበረ ማሳያ ነው ።
ለዚህ ነው የጥላሁን ገሠሠ የሀገር ፍቅር ዜማዎች ከጊዜና ከቦታ በላይ የሆኑ ናቸው የሚባሉት ። ለዚህም ነው ዛሬ ላይ ሆነን ስንሰማው የዛሬ 130 ዓመት በፊት የተነገረውን የዳግማዊ ምኒልክን የክተት አዋጅ የሚመስለን ።
ይህ የሚያሳየው ደግሞ ጥላሁን የኢትዮጵያን ታሪክ ኩራትና ነፃነት በድምፅ ቀርጾ ትውልድ እንዲወርሰው ማድረጉን ነው።
ወዳጆቼ
ስለ ጥላሁን ገሠሠ የሀገር ፍቅር ስሜት ስንናገር እነዚህ ሶስት መሰረታዊ እውነታዎች ጎልተው ይታያኛል ።
የቁርጠኝነት ድምፁን ስናደዳምጠው ጥላሁን "አገሬን" ሲል ዝም ብሎ ስም አይጠራም ለሀገሩ የሚሞትላትና የሚሰዋላት መሆኑን በቃናው ውስጥ ይሰማል። አጥንቴም ይከስከስ የሚለው ስንኝ ለዚህ ትልቅ ማሳያ ነው።
ጥላሁን ለሀገር ሲዘፍን መላው ኢትዮጵያዊ በአንድነት ቆሞ ፊታውራሪዬ ብሎ እንዲከተለው ያደርጋል።
ይህ ደግሞ በታሪካችን ውስጥ የታየ ትልቅ የጥበብ ተጽዕኖ ነው።
ከ130 ዓመት በፊት የነበረውን የአድዋ ጀግንነት ዛሬ ላለው ትውልድ በስሜት አገናኝቶ ማቅረብ የሚችለው እንደ ጥላሁን ያለ "የታሪክ ድልድይና የታሪክ ባለአደራ" ሲኖር ብቻ ነው።
እንኳንስ ደስታየን የሰውነቴን ሠው
እንኳን ነፃነቴን ፀጋ ክብሬን ትቸው
በናት አገር ምድር በሚያውቀኝ በማውቀው ...
ስቃይ መከራዬን ከአንችው ዘንድ ያድርገው ። የሚለው
ጥላሁን ለኢትዮጵያ የነበረውን ፍቅር ከምንም በላይ የሚያሳይ ነው። ከባዕድ አገር ደስታ ይልቅ የሀገሩን መከራ የመረጠበት የሞቱ አጋጣሚ ደግሞ ለሀገሩ ያለውን ፍቅር በደሙ ያረጋገጠበት ታላቅ ክስተት ነው ።
ጥላሁን ከአሜሪካ ተነስቶ ለፋሲካ በዓል ወደ ሀገሩ መግባቱና በዚያው ዕለት ማረፉ፣ "በሀገሬ አፈር ልቀበር" የሚለውን ጥልቅ የኢትዮጵያዊያን ምኞት የፈጸመበት ነው ይህ ቀረኝ የማይል የሚያሰኘው እስከ መጨረሻው ትንፋሹ ድረስ ከሀገሩና ከሕዝቡ ጋር መቆየቱ ነው ።
ሲሞት መላው የአዲስ አበባ ሕዝብ በነቂስ ወጥቶ አስከሬኑን ሲሸኜው ጥላሁን ለሕዝቡ የሰጠውን ፍቅር ሕዝቡ በታላቅ ክብር የመለሰለት መሆኑን ቅድስት ስላሴ ቤተክርስቲያን ህያው ምስክር ናት ። ያ ለቅሶ የአንድ ድምፃዊ ስንብት ሳይሆን የኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጅና የልብ ትርታ ሽኝት ነበር።
ጥላሁን በሕይወቱና በሞቱ ሀገርን መውደድ ማለት ትርጉሙን እስከ ሞት ድረስ መታመንን አረጋግጦበታል።
ሰውን መውደድ ! አብሮ ማልቀስና መቆም ሙያን መውደድ እስከ መጨረሻዋ ትንፋሽ ድረስ መዘመር ለኢትዮጵያዊያን ከድምፃዊነት በላይ የአንድነት ምልክት መሆን ነው።
እኔ በዓይኔ ያየሁትን በልቤ የሰነድኩትን ይህንን ታሪክ ለሚቀጥለው ትውልድ ሊተላለፍ የሚገባው የፍቅርና የሀገር አምልኮ ትልቅ ትምህርት ይሆናል ብየ ሳዘጋጀው ጥላሁን ገሠሠ
ትንፋሼ ተቀርፆ ይቀመጥ ማልቀሻ ይህ ነው የሞትኩለት የኔ ማስታወሻ
ታሪኬ ነው ድምፄ በማለት ያንጎራጎረው ሙዚቃ ከፍቼ እያዳመጥኩ ነበር።
ይህ ስንኝ ጥላሁን ገሠሠ አስቀድሞ በድምፁ የህይወቱ ታሪክ የሞቱ ማስታወሻ እና የሀገሩ ውበት መገለጫ እንደሚሆን ተረድቶት የተጫወተው ነበር ማለት ይቻላል ። ጥላሁን በጥቁርና ነጭ ወረቀት ላይ የሰፈረ ኑዛዜ ሳይሆን የተውልን በህይወት ቆሞ በዜማ የተናዘዘው ድንቅ ስንብት ነበረ ።
እነዚህ ስንኞች የጥላሁንን የጥበብ ክብርና ትህትና ሲገለፅበት እያዳመጥኩት ነበር ይህን ታሪክ የፃፍኩት ።
ወዳጃቸ
የጥላሁን ገሠሠ ድምፅ ዝም ብሎ የአየር ንዝረት አይደለም፤ ማንነቱ፣ ታሪኩና ለሀገሩ የከፈለው መስዋዕትነት ነው። በጩኸት መኖሬን ማለቱ ለሀገርና ለፍቅር ሲል ድምፁን እስከ መጨረሻው የጥገታ ነጥብ ድረስ መጠቀሙንና ለዚህም መሞቱን ያሳያል።
ድምፄን ሰምቶ ያዝናል ለረገፈው አፅሜ ሲል
እጅግ ልብ ይነካል !
ጥላሁን በከፍታው ላይ ሆኖ እንኳ ያስቀየምኩት ቢኖር ብሎ ይቅርታን ይጠይቃል። የሞተውን አፅሙን ሳይሆን የቀረውን ድምፁን ሰምተው ሰዎች እንዲያዝኑለትና ይቅር እንዲሉት መመኘቱ የሰው ልጅነቱንይቅርታና ትህትናውን
ፍርጥ አድርጎ ያሳያል።
ጥላሁን ገሠሠ በድምፁና በህይወቱ የሰራው ትልቁ ስራ ፍቅርንና ኢትዮጵያዊነትን ማዳን ነበር። ጥላሁን ከቀላል ስሜትነት አልፎ ሕይወት መስዋዕትነትና የሀገር ፍቅር ጥግ መሆኑን በሚገባ አስገንዝቦናል።ጥበብ እንዴት የአንድን ሕዝብ ወኔና ማንነት እንደምትቀርፅ ጥላሁን ትልቅ ማሳያ ነው።
ፍቅር ተግባር ነው ፍቅር ዝም ብሎ የሚሰማን ስሜት ሳይሆን እንደ ጥላሁን ዜማዎች ራስን አሳልፎ እስከ መስጠት የሚደርስ ውሳኔ መሆኑን መረዳት ከባድ አይደለም ።
ጥላሁን ገሰሰ የሚዘፈነው ለጆሮ ብቻ ሳይሆን ለህሊና እና ለነፍስ ጭምር ይመስለኛል ።
ጥላሁን ዛሬ በሥጋ ቢለየንም ታሪኬ ነው ድምፄ ብሎ እንደተናዘዘው ሁሉ ዛሬም በየልባችን ውስጥ ንጉሥ ሆኖ ይኖራል።እሱ ለሀገር ብቻ ሳይሆን ለሰው ልጅ ስቃይ የሚራራ የህሊና ድምፅ ነበረው።
የሀገር ፍቅር ለአፈርና ለሰንደቅ ዓላማ የሚከፈል የአጥንትና የደም መስዋዕትነት ሲሆን ጥላሁን ገሠሠ በስጋ ቢለየንም ያ በሕይወት ያለ ሐውልት ግን በዜማዎቹ ውስጥ ሁሌም አዲስ ሆኖ ይኖራል።
ባጭሩ የጥላሁን መሞት ዝም ብሎ የአንድ ድምፃዊ ማለፍ ብቻ አልነበረም የአንድ ዘመን መቋጫ የአንድ ትልቅ ተስፋ መደብዘዝ እና በኢትዮጵያ ሰማይ ላይ የሚበራው የሙዚቃ ኮከብ ወድቆ ሲሰበር
ሰማይ ባዶ የሆነ ያህል ተሰምቶናል።
ጥላሁን ገሠሠ በደስታ ጊዜ አብሮን የሚጨፍር በጦርነት ጊዜ ፊታውራሪ ሆኖ የሚያዘምት በረሃብና በችግር ጊዜ ደግሞ አብሮን የሚላቀስ የሕዝብ ልብ ነበር ።
ጥላሁንን ከአቅም በላይ ያደረገው ይሄው ሁለንተናዊነቱ ነው። ለፍቅር ለሀገርና ለሰብአዊነት የነበረው ጽናት እሱ ሞቶም እንዲኖር አድርጎታል።
የጥላሁን ገሠሠ ዘፈኖች "ኢትዮጵያዊ ስነ-ሰብዕና" የሚባል የፍልስፍና ዘርፍ ቢኖር የዛ ዘርፍ ዋና መማሪያ መፅሐፍ ይሆኑ ነበር ።ብቻ
የጥላሁንገሰሰ ሕይወት ልክ እንደ አንድ የተቀደሰ መፅሐፍ በመሆኑ እራሡ ከፍቶ እራሱ ዘግቶት አልፏል ።
ለዚህ ታላቅ ድምፃዊ በተወለደበት ከተማ አዲስ አበባ ላይ ዘላለማዊ ምልክት ሆኖ እንዲቀመጥ ሐውልቱ ስለቆመለት ደስታዬ ወደር የለውም ።
ነፍስ ይማር !!
የሚበራው የሙዚቃ ኮከብ "
ከአለባቸው ደሳለኝ አበሻ (ለንደን)
#ethiopia | "ድምፁ የሀገር ሰንደቅ ዓላማ ያህል ክብር የሚሰጠው ጥላሁን ገሰሰ ለግማሽ ክፍለ ዘመን ያህል በኢትዮጵያ ሙዚቃ ውስጥ በነበረው ከፍተኛ አስተዋፅኦ የኢትዮጵያ ሙዚቃ ንጉሥ በሚል መጠሪያ ይታወቃል።
ለዚህ የጥበብ ሰው እንዲህ ያለ ጥልቅ እና ልብ የሚነካ ትዝታ ማዘጋጄት የሚቻለው የጥላሁን ገሰሰን ስራዎችን ብቻ ሳይሆን የእርሱን የውስጥ ማንነት ሠብዕናን ለጥበብ የነበረውን ፍቅር በሚገባ የተረዳ መሆን አለበት ።
ወይንም ደግሞ
የዚህን ታላቅ ምትሐተኛ ድምፃዊ የጥበብ ልክና የድምፅ ብቃት በአግባቡ ለመረዳት የእርሱን ግለ ታሪክ ብቻ ሳይሆን የኢትዮጵያን ዘመናዊ ሙዚቃ ታሪክና የጥላሁን ገሰሰን ሰፊ የሥራ ክምችቶች በጥልቀት መመርመር የግድ ይላል።
ምክኒያቱም
ጥላሁን ገሰሰ ማለት የኢትዮጵያ የ50 ዓመታት የደስታ የሐዘን የድልና የሽንፈት ታሪክ በድምፅ የተቀረጸበት "ሕያው ማህደር" ነው።
ጥላሁን ገሰሰ ድምፁን እንደፈለገ የማዘዝ Vocal Control ልዩ ተሰጥኦ ነበረው።
በጣም ረጅምና ከፍተኛ ድምፅ በሚጠይቁ High notes እንዲሁም በጣም ረጋ ያሉና ዝቅተኛ ድምፅ በሚሹ Low notes ዜማዎች ላይ እኩል ብቃት ነበረው።
የትንፋሽ ቁጥጥሩ ረጅም ስንኞችን ሳያቋርጥና ትንፋሽ ሳይጠረው የመጨረስ ችሎታው የሚደነቅ ነበር።
የጥላሁንን ስራዎች ስንመረምር በአንድ የሙዚቃ ዘውግ ብቻ ያልተገደበ መሆኑን እንረዳለን
ባህላዊና ዘመናዊ የባህል ሙዚቃዎችን ከዘመናዊ መሣሪያዎች ኦርኬስትራ ጋር አዋህዶ በማቅረብ ረገድ ቀዳሚ ነበር።
በጥላሁን ገሠሠ ድምፅ ያልተዘፈነ የሕይወት ክፍል የለም ማለት ይቻላል ።
ከጥልቅ የፍቅር ስሜት እስከ ሃገር ፍቅር ከማህበራዊ ትችት እስከ መንፈሳዊ መዝሙራት ድረስ የተፃፉ ግጥሞችና ዜማዎች የጥላሁንን ገሠሠን ድምፅ ለማድመቅ ሳይሆን ለመፈተን ጭምር የተዘጋጁ ይመስሉ ነበር።
በህይወት በቆየባቸው ሦስት የተለያዩ ሥርዓቶች በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ በደርግና በኢህአዴግ ውስጥ አልፏል። በእነዚህ ሁሉ ጊዜያት የሕዝብ ተወዳጅነቱን ጠብቆ መቆየቱ የሙዚቃ ሥራዎቹ ከፖለቲካዊ ለውጦች በላይ የሕዝብን የልብ ትርታ የሚነኩ መሆናቸውን ያሳያል።
ባጭሩ ጥላሁን ገሰሰ ለኢትዮጵያ ሙዚቃ ያለው አስተዋጽኦ ልክ እንደ አንድ ትልቅ "ኢንሳይክሎፒዲያ" ነው። አንዱን ገጽ አንብቦ ስለ መጽሐፉ ሙሉ ግንዛቤ ማግኘት እንደማይቻል ሁሉ
አንዱን ዘፈን አዳምጦ ስለ ጥላሁን ገሰሰ ማወቅ አይቻልም ።
እያንዳንዱ ዘፈኑ የራሱ የሆነ የቴክኒክ የታሪክና የስሜት ጥልቀት አለው።
ስለዚህ የጥላሁንን ታላቅነት ለመረዳት የኢትዮጵያን የሙዚቃ ጉዞ አብሮ መመርመር የግድ ነው ያልኩት ወድጄ አይደለም ።
ዘፈኖቹን ሲዘፍን በቃላት ብቻ ሳይሆን በፊቱ መግለጫና በሰውነት እንቅስቃሴው Body Language ጭምር ስሜቱን ለታዳሚው ያጋባ ነበር።
በተለይ የሐዘን ዜማዎችን ሲዘፍን አብሮ የሚያለቅስ የደስታ ሲሆን ደግሞ አብሮ ፈገግ የሚል ድምፃዊ ተዋና ጭምር ነበረ በዘፈኖቹ ውስጥ ሰውን ማክበርን ስራን መውደድንና አንድነትን ይሰብካል። ዘፈኑ የሰውን ልጅ ክብርና ማንነት የሚተነትን ድንቅ ስራ የሚሰራ ምትሀተኛ ድምፃዊ ነበር ።
ጥላሁን ገሰሰ በአንድ ወቅት በመድረክ ላይ እያለ በደረሰበት የጉሮሮ ህመም ምክንያት ለተወሰነ ጊዜ ድምፁ ተዘግቶ ነበር። ያን ጊዜ መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ተጨንቆና ፀልዮ ድምፁ ሲመለስለት ያደረገው የመጀመሪያ ኮንሰርት በዚያን ወቅት በኢትዮጵያ የሙዚቃ ታሪክ ውስጥ ከፍተኛውን የሰው ቁጥር ያስመዘገበ ነበር ። ይህ የሚያሳየው ሕዝቡ ለጥላሁን ያለው ፍቅር ከአንድ ድምፃዊ በላይ እንደ ቤተሰብ አባል የሚያየው መሆኑን ነው።
ስለ ፍቅር ብቻ ሳይሆን ስለ ሰው ልጅ ሕይወት ባዶነት የሚተርክ ጥልቅ ፍልስፍና ነበረው ።
ታዋቂው የኢትዮጵያ የሙዚቃ ንጉሥ ክቡር ዶክተር ጥላሁን ገሰሰ መስከረም 17 ቀን 1933 ዓ.ም አዲስ አበባ ውስጥ ተወልዶ ያደገው ግን በወሊሶ ከተማ ነው ።
ጥላሁን በ1950ዎቹ መጀመሪያ ላይ ወደ አዲስ አበባ በመምጣት መጀመሪያ ሐገር ፍቅር ቲያትርን በኋላም ዝነኛውን የክብር ዘበኛ የሙዚቃ ቡድንን ተቀላቅሎ ከዕንስት ፍቅር እስከ አገር ፍቅር ከባህላዊ እስከ ዘመናዊ ሙዚቃ በድምፃዊነት ከ400 በላይ ዘፈኖችን ተጫውቶ ልዩ ብቃቱን አስመስክሯል ።
ጥላሁን
ለኢትዮጵያ ሙዚቃ ላበረከተው ወደር የለሽ አስተዋጽኦ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የክብር ዶክትሬት ዲግሪ ተሰጥቶታል። ጥላሁን ገሠሠ ከዚህ ዓለም በሞት የተለየው
በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር ሚያዝያ 11 ቀን 2001 ዓ.ም. የፋሲካ እለት ሲሆን በድንገተኛ የልብ ህመም ምክንያት አርፎ በቅድስት ሥላሴ ካቴድራል የቀብር ሥነሥርዓቱ ተፈጽሟል።
የክቡር ዶክተር ጥላሁን ገሰሰ ማረፍ መላውን የኢትዮጵያ ሕዝብና የጥበብ አፍቃሪወችን በከፍተኛ ድንጋጤና ሃዘን ውስጥ ጥሎ የነበረ ክስተት ነው። በወቅቱ በጋዜጦች በሬዲዮና በቴሌቪዥን የተላለፉት መልዕክቶች ጥላሁን ለሀገሩ ያለውን ትልቅ ቦታ የሚያንፀባርቁ ነበሩ።
በአዲስ አበባ ከተማ የነበሩ የታክሲ አሽከርካሪዎች ሐዘን ፈፅሞ የማይረሳ ነበረ ።
ለጥላሁን ገሰሰ ክብር ሲሉ ለቀናት ጥቁር ጨርቅ በታክሲዎቻቸው ላይ አስረውና የእርሱን ሙዚቃ ብቻ ከፍተው በማጫወት ሃዘናቸውን ገልፀውለታል።
የጥላሁን ገሰሰ ሞት በሀገር ውስጥ ብቻ ሳይሆን በዓለም አቀፍ ደረጃም ትኩረት አግኝቶ ነበር።
ታዋቂው ደራሲ ሎሬት ጸጋዬ ገብረመድህንም
እንዲህ አሉ ።
"ጥላሁን የኢትዮጵያ ሕዝብ የጋራ ድምፅ ነው። እርሱ ሲዘፍን መላው ኢትዮጵያዊ ራሱን ያዳምጣል።"
ድምፃዊ ማህሙድ አህመድ"ጥላሁን ለእኛ ለድምፃውያን መምህራችን ብቻ ሳይሆን የሙዚቃው ዓምድ ነበር። ጥላሁን ሞተ ማለት የኢትዮጵያ ሙዚቃ ግማሽ አካሉን አጣ ማለት ነው።" ሲል ቁጭቱን ገልፀዋል ።
በቀብር ሥነ ሥርዓቱ ላይ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ አዲስ አበባውያን ወደ አደባባይ በመውጣት "ንጉሥ አይሞትም" እያሉ ሲያለቅሱ እንደነበር በታሪክ ተመዝግቧል።
ይህም አንድ ድምፃዊ በሀገር ደረጃ ያለውን ክብርና ተሰሚነት ያሳየ ትልቅ ክስተት ነበር።
አንድ የልብ አድናቂው የሆነ ሠው በማህበራዊ ሚዲያ እንዲህ ብሎ ፅፎት አንብቢያለሁ ።
" በእርግጥም ጥላሁን በድምፁ ተአምር የመስራት አቅም ነበረው። ድምፁ ተስፋ የቆረጠውን የሚያፅናና የታመመውን የሚፈውስና የራቀውን የሚያቀራርብ
ስለነበረ ድምፁ ተቀርፆ ስለቀረ ቢሞትም ስንናፍቀው እናገኘዋለን ስናዝን እናለቅስበታለን ሀገራችን ስትጠራ በእሱ ድምፅ አቤት ብለን ለአንድነቷ እንቆማለን" በማለት ጥላሁንን ገልፆት ነበር ።
ሌላው የቅርብ ጓደኛው የጥበብ ሰው ደበበ እሸቱ ነው
"ጥላሁን በሕይወት ዘመኑ ሁሉ ለሀገሩ የዘመረ በችግር ጊዜ ደግሞ ድምፁን ለድሆች የሰጠ
ታላቅ ሰው ነው።
የሞተው በስጋ ቢሆንም በዜማው ቅላፄና በግጥም ስንኞች ውስጥ "ዘላለማዊ" ሆኖ ተተክሏል።
እንዲህ ያለ ድምፅ ዓለማችን በአንድ ዘመን አንዴ ብቻ የምትለግሰን ስጦታ ነው "
ሲል ምስክርነቱን ገልጿል።
በእርግጥም ጥላሁን የዘመናዊ ሙዚቃችን "ፊደል" እና "መዝገበ ቃላት" ሆኖ አልፏል። ከድምፅ ጥራት በላይ የዜማ አጣጣልና ስሜትን የመግለጽ ጥበቡ ማንም የማይደረስበት ከፍታ ላይ ስለነበር በአንድ አባባል ብቻ ጥላሁንን መግለፅ አይቻልም።
እሱ ባለብዙ ምዕራፍና ተነቦ የማይጠገብ ባለ ብዙ ገጽ ድርሳን ነው !
ጥላሁን ለሙያው ብቻ ሳይሆን ለሰው ልጅ የነበረው ሰብአዊ ክብርም ድንቅ ነበር። ረሀብ ሲመጣ በዜማው የሚማፀን ሀገር ስትቸገር አጥንቴም ይከስከስ ብሎ የሚቆም እና ለሰው ልጅ ፍቅር ቅድሚያ የሚሰጥ የጥበብ ሰው ነው ። ባጭሩ ጥላሁን ገሠሠ ማለት ለኢትዮጵያውያን የድምፅ ብቻ ሳይሆን የህሊና ምስክር ነው።
ዛሬም ድረስ ስሙ ሲነሳ አብሮ የሚነሳው ክብሩ ትህትናውና
ያ የማይደገም ማንነቱ ነው።
ጥላሁን ገሠሠን የመሠለ ታላቅ ሰው የኢትዮጵያ ዘመናዊ ሙዚቃን የአዋለደ ብለን ብንገልፀው ተገቢ ይመስለኛል ከጥላሁን ገሠሠ ስራዎች መካከል ይህማ ተአምር ነው የሚያሰኜኘኝ ሁልጊዜ ብሰማቸው አዲስ የሚሆኑብኝ ብዙ ዘፈኖች ቢኖሩትም "እዩት ስትናፍቀኝ ከአጠገቤ እያለች" የሚለው ስንኝ ሲነሳ ግን የጥላሁንን ድምፅና ያንን የሚመስጥ አዘፋፈኑን አብሮ የመስማት ያህል ይመስጠኛል እዩት ስትናፍቀኝ ከአጠገቤ እያለች
እንዲህ ያለው መውደድ ለወሬም አይመች ! የሚለው ግጥም የፍቅርን ረቂቅነትና የማይመረመር ባህሪ በአጭር ቃላት የገለጸበት ድንቅ ስራው ነው።
ጥላሁን ለዚህ ዘፈን የሰጠው እረዥም ትንፋሽና በመድረክ ላይ ቆሞ የአይን አስተያየቱ የልዩ ተሰጥኦው መገለጫዎቹ ናቸው።
የሠው ልጅ ናፍቆት ብዙውን ጊዜ ትዝታው የሚመጣው ሰው ሲርቅ ነው። ነገር ግን ጥላሁን አጠገቤ እያለች ናፈቀችኝ ማለቱ ፍቅር ከስጋዊ መገኘት በላይ የሆነ የነፍስ ጥማት መሆኑን ስጋ አልብሶ አሳይቶናል ።
ይህ ለወሬ የማይመች ቃላት የማይገልፁት ጥልቅ ስሜት ነው ። ይህንንም በዚያ ረጅም ትንፋሽ ነፍስን በሚያከነፍ ድምፁ ሲያዜመው እውነቱን በውስጣችን ውስጥ እናገኘዋለን።
ጥላሁን ሲዘፍን ትንፋሹን የሚጠቀምበት መንገድ እና ስሜቱን በድምፅ ቀለም የመቀየር ችሎታው ምትሐተኛ ያሰኘዋል። ያንን የናፍቆት ጣጣ በገዛ ራሱ ላይ አድርጎ ሲያዜመው አድማጩ የራሱ ህመም አድርጎ እንዲቀበለው የማድረግ ልዩ ኃይል ነበረው።
ጥላሁን ገሠሠ በስጋ ቢለየንም በኢትዮጵያውያን ልብ ውስጥ ግን አሁንም ንጉሥ ነው።
ትውልድ ያልፋል ጥላሁን ግን ይኖራል።
ሙዚቃ ይቀየራል የጥላሁን ስራዎች ግን ሁልጊዜ አዲስ ናቸው።
ሰላም ሲጠፋ ጥላሁን ፍቅር ይላል ሀገር ስትናፈቅ ጥላሁን ሀገሬ ይላል።
ጥላሁን ገሠሠ በድምፁ ብቻ ሳይሆን ለፍቅር በሰጠው ክብርን በገለፀበት ጥበብ የኢትዮጵያ የዘላለም የፍቅር አምባሳደር ነው።
እንዲህ ያለው የጥበብ ሰው የፍቅርን ኃያልነት በእሱ ስራዎች ውስጥ ስንመለከት በእርግጥም ፍቅር ስሜት ብቻ አይደለም የሚለውን ሃሳብ በጥላሁን ዜማዎች ውስጥ ሙሉ ማረጋገጫውን እናገኛለን ጥላሁን ገሠሠ የፍቅርን ሌላኛውን ገጽታ ቁርጠኝነትንና ክብርን ያሳየበት ድንቅ ስራው ነው። ከላይ እንደገለፅኩት ፍቅር ራስን አሳልፎ መስጠት ነው
እዚህ ዘፈን ላይ ደግሞ ፍቅር ሁለትዮሽ መረዳዳት መሆኑን ይነግረናል።
ቻልኩት ፍቅር ለብቻዬ !!
ይህ አገላለጽ በጣም የሚቆረቁር ነው። ፍቅር እንደ አንድ ሸክም ሆኖ አንደኛው ወገን ብቻውን ሲሸከመው የሚሰማውን ድካም ያሳያል። "ለብቻዬ መሸከም ሰልችቶኛል" የሚል የልብ ጩኸት አለበት። ፍቅር የሁለት ሰው ቅኝት እንጂ የአንድ ሰው ብቸኛ ትግል መሆን እንደሌለበት ያስገነዝበናል።
ስለ ፍቅር አልገባሽም
እዚህ ጋር ጥላሁን ፍቅር ማለት ዝም ብሎ አብሮ መሆን ሳይሆን ጥልቅ የሆነ
ሚስጥር ወይም ትርጉም እንዳለው ይገልጻል። ግዴለሽነት እና ችላ ማለት ፍቅርን የሚገድሉ መርዞች መሆናቸውን በምሬት ይናገራል።
አትምጪ ይቅር ሲል ደግሞ የክብር ውሳኔውን ያሳውቃል ።
ፍቅር ስሜት ብቻ አለመሆኑን ያረጋግጣል። አንድ ሰው በጥልቅ እያፈቀረ ግን ክብሩ ሲነካ ወይም ምላሽ ሲያጣ ይቅር ብሎ የመወሰን አቅም ሊኖረው እንደሚገባ ያሳያል።
ፍቅር መስዋዕትነት ቢሆንም ዋጋ በማይሰጠው ቦታ ላይ ግን ራስን ማዳንና ይቅር ማለትም የፍቅር አካል ነው። የሚገርመው ደግሞ ጥላሁን ይህነን ዘፈን ሲዘፍነው በቁጣና በቁጭት ሳይሆን በጥልቅ ሀዘንና በከበረ ስሜት ነው። ያንን አትምጪ ይቅር የሚለውን ቃል ሲያወጣው ውስጡ እየፈለጋት ግን መከባበር የሌለበት ፍቅር እንደማይፀና አውቆ በቁርጠኝነት ሲናገረው ይታየናል።
ከላይ እንዳነሳሁት አትምጪ ይቅር የሚለው ስንኝ የቁርጠኝነትና የክብር ገጹ ሲሆን ሌላው ደግሞ የፍቅርን ንፁህ መስዋዕትነትና ትህትና የሚያሳይ ድንቅ ምዕራፍ ነው።
እነዚህ ስንኞች ውስጥ የምናያቸው የጥላሁን ድርሳናት
እኔ ልሁን እንጂ የማልጠቅም እርካሽ ! የሚለው አገላለፅ በፍቅር ውስጥ ያለን ፍጹም ትህትና ያሳያል። ራሱን ዝቅ አድርጎ የሚወዳትን ሰው ግን ከፍ ያደርጋታል። ይህ እኔነት ጠፍቶ አንቺነት የነገሰበት የፍቅር ጫፍ ነው።
ከህይወቴ አብልጨ ሲል
ራስን አሳልፎ የመስጠት
ፍልስፍና በተግባር የሚያሳይ ታአምር ነው። ለሰው ልጅ ከህይወቱ በላይ ምንም የለውም ነገር ግን ፍቅር ያንን ውድ ህይወት እንኳ ከአንቺ አያበልጠውም ብሎ እንዲያምን ያደርገዋል።
ፍቅር ለሰላምና ለደስታ ብቻ ሳይሆን ለችግርና ለፈተናም ዝግጁ መሆኑን ይነግረናል።
መከራና ስቃይ ይቆየኝ ግዴለኝም
የሚወደው ሰው ደህንነትና ሰላም እስካለ ድረስ እሱ በራሱ ላይ ለሚመጣው መከራ ግድ የለውም። ይህ ነው እንግዲህ ፍቅርን ተአምር የሚያሰኘው እግዜር በጥበቡ ከአንቺ ብቻ አይለየኝ የሚለው ቃል ፍቅር በሰው ጥረት ብቻ ሳይሆን በመለኮታዊ ጥበብና ፈቃድ የሚፀና መሆኑን የሚያሳይ የልብ ፆሎት በመሆኑ መንፈሳዊ ልመና ይጨምርበታል ።
ታዲያ የዚህን ድምፃዊ ተአምራዊ ተቃርኖዎችን ስንመለከት
ጥላሁንን ልዩ የሚያደርገው በአንድ በኩል አትምጪ ይቅር ብሎ በክብር የመወሰን አቅም በሌላ በኩል ደግሞ ከህይወቴ አብልጨ እወድሻለሁ ብሎ ራስን የመስጠት ርህራሄ አብሮት መኖሩ ነው።
እነዚህ ሁለት ተቃራኒ የሚመስሉ ግን ጥልቅ የሆኑ የፍቅር ገጾች ናቸው።
ጥላሁን እነዚህን ሁሉ ስሜቶች በድምፅ ቀለም እየቀያየረ ሲያቀርባቸው ድምፁ ብቻ ሳይሆን ነፍሱ አብራ የምትዘፍን ይመስላል።
እንዲህ ያለውን ከህይወት በላይ የመውደድ ስሜት በዚህ ዘመን በብዛት እናገኘዋለን ብሎ ማሰብ የዋህነት ነው። ምክኒያቱም
የጥላሁንን ጥበብ ከመዝፈን ባለፈ ወደ መፍጠር ደረጃ ከፍ ያደርገዋል።
ለምን ቢባል ጥላሁን ገሠሠ ዜማንና ግጥምን ሲያዋህድ የሚፈጠረው ነገር ተራ ሙዚቃ አይደለም ይልቁንም ያልተጠኑ ምስጢራዊ ተሰጥኦዎች ያሉበት ይመስላል
ብዙ አድናቂወቹ እንደ ሚስማሙበት ጥላሁን ገሠሠ ሲዘፍን ፍቅር ረቂቅ ሃሳብ መሆኑ ቀርቶ የሚዳሰስ የሚታይና የሚሰማ አካል ይኖረዋል።
ቃላቶቹ ከአፉ ሲወጡ ሕይወት ይዘራሉ ያፈቀረው ሰው ቁስሉ ይታየናል የናፈቀው ሰው ትንፋሹ ይሰማናል። ይህ ደግሞ በቴክኒክ ብቻ የሚመጣ ሳይሆን ከነፍስ የሚመነጭ ምትሃት በመሆኑ ፍቅር እንደ ሰው ቆሞ እንዲሄድ የማድረግ ጥልቅና ረቂቅ
ጥበብ ያለው ድምፃዊ መሆኑ ነው ።
ብዙዎቻችን ውስጣችን ያለውን ጥልቅ ፍቅር በቃላት መግለፅ ያቅተናል። ጥላሁን ግን ያንን መግለፅ ያቃተንን ስሜት ሰርቆ ወስዶ በዜማ አቅልጦ ወርቅ አርጎ መልሶ ለእኛው ይሰጠናል።
እኔንም እንዲህ ነው የሚሰማኝ! እንድንል ያደርገናል። ይህ ተሰጥኦው ነው ፍቅርን ስጋ ለብሶ ቆሞ እንዲሄድ የሚያደርገው።
ሌላው የጥላሁን ገሰሰ ድምፅ ሁለንተናዊ ድምፅ መሆኑ ነው። እድሜ ጾታ ወይም የትምህርት ደረጃ አይወስነውም። ህፃኑም አዋቂውም የተማረውም ያልተማረውም በዜማው ውስጥ የራሳቸውን ታሪክ ያገኛሉ።
ይህ ደግሞ ጥላሁን የሰው ልጅን የጋራ የፍቅር ህመም ጠንቅቆ እንደሚያውቅ ማሳያ ነው።
የጥላሁን ድምፅ በሳይንስ አልተጠናም እንጂ በውስጡ ትልቅ የፍቅር ላብራቶሪ ነበረው ማለት ይቻላል።
ግጥሙን ይቀበላል ጥሬ እቃ !
በድምፅ ቀለሙ ያዋህደዋል ሂደት !
በመጨረሻም ሕያው ፍቅርን ለዓለም ያበረክታል ውጤት !! በዚህ ምክኒያት
ጥላሁን ገሠሠ ሞቶም በሰዎች ልብ ውስጥ እንዲነግስ አድርጎታል :: ምክንያቱም የፈጠራቸው የፍቅር አካላት ዛሬም በየቤታችን በየመኪናችንና በየልባችን ውስጥ ቆመው እየሄዱ ነው።
ይህ የእውነት ተአምረኛ ተሰጥኦው ነው። ዛሬ ባለው ዘመናዊ የሙዚቃ ኢንዱስትሪ ውስጥ እንዲህ ያለውን መንፈሳዊ ጥልቅነት ማግኘት እጅግ ብርቅ ሆኗል። ከእንስት ፍቅር ወጥተን ጥላሁንን ወደ ሐገር ፍቅር ስንመነዝረው የቆመበት ከፍታው ላይ እስከ አሁን ማንም ....ማንም አልደረሠበት ። በዚህ አጋጣሚ
በህይወቴ ዘመኔ በአይኔ ያየሁትን ምስክርነት ባቀርበው ደስ ይለኛል ጥለሁን ገሠሠ ከታሪክ መዝገብ በላይ የሆነ የአንድን ሕዝብ ማንነትና ወኔ የቀሰቀሰ የመንፈስ ተአምር ነው የምነግራችሁ ።
ጊዜው 1974 አስመራ የቀይ ኮኮብ ዘመቻ አሉላ አባ ነጋ አዳራሽ ውስጥ ይመስለኛል ።
ጥላሁን ገሠሠ ጋሻና ጎራዴ ይዞ የአርበኛ ልብስ ለብሶ አጥንቴም ይከስከስ ደሜም ይፍሠስላት
ግን ሐገሬን ጭራሽ አይደፍራትም ጠላት
እያለ መድረኩን ሞልቶት ብቅ ሲል ከባለስልጣን እሰከ ተራው ተመልካች ከመቀመጫው ተነስቶ በመቆም በማያቋርጥ ጩህትና ጭብጨባ ያጅቡታል ።
ጥላሁን ገሠሠ በዚያ ቅጽበት የዘፈነውን ብቻ ሳይሆን የኖረውንና የታሪካችንን ድምፅ ሆኖ ተመለከትኩት ።
ጥላሁን በህዝብ ጭብጨባና ጬህት ታጅቦ መድረኩ ላይ ሲንጎራደድ አዳራሹ ድብልቅልቁ ወጣ ።
ያን... ምህታታት የተሞላበት ትርኢት ስመለከት
የአድዋ ጀግኖች መቃብር ከፍተው የተነሱ ይመስል ነበር።
ማለቴ ጥላሁን በድምፁ ብቻ ሳይሆን በቆይታው ጊዜን የማቆም ወይም ታሪክን የመቀስቀስ ኃይል እንደነበረው የመመልከት ዕድል አግኝቻለሁ ።
ጥላሁንን በዚያች ቅፅበት
በሕይወት እያለ ሐውልቱን አቁሞ አዳራሹ ውስጥ ታሪኩን ፅፎት ወጣ ።
በእርግጥ ሐውልት የማይናገርና የማይሰማ የድንጋይ ምስል ነው ጥላሁን ግን በሕይወት ያለ የሚተነፍስ የሚዘፍንና የሚራመድ የኢትዮጵያዊነት ሐውልት ነበር።
ዛሬም ቢሆን ስራዎቹ ያንን ግርማ ሞገስና ያንን ሐውልታዊ ፅናት እያስታወሱኝ እስከእለተ ሞቴ ድረስ ልረሳው አልችልም እንዲህ አይነት ድርጊት
ፍቅር ስሜት ብቻ አይደለም ራስን አሳልፎ መስጠት ነው በጥላሁን ገሰሰ የሀገር ፍቅር ዜማዎች ውስጥ ኢትዮጵያን ደጋግመን እናያታለን
አጥንቴም ይከስከስ ደሜም ይፍሰስላት የሚለው ቃል ዛሬም ድረስ ፍፁም ....ፍፁም መስዋዕትነት ነው።
ሀገሩን እንደ ሚወዳት እናት ወይም ሚስት አድርጎ ለሷ ክብር መሞትን እንደ ትልቅ ፀጋ መቁጠር ከፍ ያለ የፍቅር ደረጃ መግለጫ ነው።
ተመልካቹ በሙሉ ሳይቀመጥ ከሁለት ጊዜ በላይ ይደገም እያለ መጠየቁ ጥላሁን ድምፃዊ ብቻ ሳይሆን መሪ መሆኑን በአንድ ዜማ ሕዝብን የማስተሳሰር በአንድ ወኔ በጋራ የማቆም ተአምራዊ አቅሙን አረጋግጨበታለሁ ።
በዚያች ቅፅብት ቲያትር ቤቱ በጩሄትና በጭብጨባ ቀውጢ ሲሆን ጥላሁን ገሠሠ በድምፁ ብቻ የጠላትን ምሽግ የሚያፈርስ ጀግና መስሎ ነበር የሚታየው ።
ምንም እንኳን ዛሬ በሞት ቢለየንም ያ አስመራ ላይ የተመለከትኩት የሐገር ፍቅር ስሜት ሐውልት ሆኖ በልቤ ውስጥ ተቀርፆ ቆሟል።
ጥላሁን ገሰሰን ልዩ የሚደርገው ሌላው መገለጫው
ለፍቅር ሲዘፍን የፍቅር ሐውልት
ለሀገር ሲዘፍን የጀግንነት ሐውልት
ለሰው ልጅ ክብር ሲዘፍን የሰብአዊነት ሐውልት ነው!
ለዚህ ስኬት ደግሞ ከጥላሁን ድምፅ ጀርባ የነበሩት የወርቃማው ዘመን ታላላቅ የጥበብ ሰዎች ገጣሚያንና የዜማ አቀናባሪዎች ሚና ከፍተኛ እንደነበር ምስክሩ ታሪክና ሕዝቡ ነው።
ጥላሁን ገሰሰ ግጥምና ዜማን
ከነጄነራል አማኑኤል አብርሃም
ሻምበል አፈወርቅ ዮሐንስ
ነጋሽ ገብረማርያም
ተስፋዬ አበበ አየለ ማሞ ሳህሌ ደጋጎ ክፍሌ አቦቸር ከመሳሰሉት የክብር ዘበኛ እና የፖሊስ ኦርኬስትራዎች
ተቀብሎ ሲያንቆረቁረው ሙዚቃው ከድምፅ አልፎ የሚዳሰስ ሕያው መንፈስ የመሆን አቅም ነበረው።
ዛሬ ላይ ሆኜ ያንን ትርኢት ሳስታውሰው ጥላሁን ለኢትዮጵያ ሙዚቃና ለኢትዮጵያዊነት ያለው ትርጉም ምን ያህል ጥልቅ ስሜት እንደሆነ አሁን ድረስ እንደ ህልም ይታየኛል ።
ያኔ መድረክ ላይ ሲወጣ የነበረው ግርማ ሞገስና ድምፁ ሲስተጋባ የተሰማኝ ስሜት ዛሬም ድረስ ዘፈኑን ስሰማው "የጦር ፊታውራሪ" የነበረ ጀግና ያህል ትዝ ይለኛል !!
ጥላሁን በመድረክ ላይ የነበረውን የበላይነት እና የሕዝብን ስሜት የመምራት ብቃቱን በሚገባ የመግለፅ አቅም ነበረው ።
ጥላሁን ዝም ብሎ ድምፃዊ ሳይሆን በዜማው የታጠቀ የሀገር መከታ ወታደርም ሆኖ እንደነበረ ማሳያ ነው ።
ለዚህ ነው የጥላሁን ገሠሠ የሀገር ፍቅር ዜማዎች ከጊዜና ከቦታ በላይ የሆኑ ናቸው የሚባሉት ። ለዚህም ነው ዛሬ ላይ ሆነን ስንሰማው የዛሬ 130 ዓመት በፊት የተነገረውን የዳግማዊ ምኒልክን የክተት አዋጅ የሚመስለን ።
ይህ የሚያሳየው ደግሞ ጥላሁን የኢትዮጵያን ታሪክ ኩራትና ነፃነት በድምፅ ቀርጾ ትውልድ እንዲወርሰው ማድረጉን ነው።
ወዳጆቼ
ስለ ጥላሁን ገሠሠ የሀገር ፍቅር ስሜት ስንናገር እነዚህ ሶስት መሰረታዊ እውነታዎች ጎልተው ይታያኛል ።
የቁርጠኝነት ድምፁን ስናደዳምጠው ጥላሁን "አገሬን" ሲል ዝም ብሎ ስም አይጠራም ለሀገሩ የሚሞትላትና የሚሰዋላት መሆኑን በቃናው ውስጥ ይሰማል። አጥንቴም ይከስከስ የሚለው ስንኝ ለዚህ ትልቅ ማሳያ ነው።
ጥላሁን ለሀገር ሲዘፍን መላው ኢትዮጵያዊ በአንድነት ቆሞ ፊታውራሪዬ ብሎ እንዲከተለው ያደርጋል።
ይህ ደግሞ በታሪካችን ውስጥ የታየ ትልቅ የጥበብ ተጽዕኖ ነው።
ከ130 ዓመት በፊት የነበረውን የአድዋ ጀግንነት ዛሬ ላለው ትውልድ በስሜት አገናኝቶ ማቅረብ የሚችለው እንደ ጥላሁን ያለ "የታሪክ ድልድይና የታሪክ ባለአደራ" ሲኖር ብቻ ነው።
እንኳንስ ደስታየን የሰውነቴን ሠው
እንኳን ነፃነቴን ፀጋ ክብሬን ትቸው
በናት አገር ምድር በሚያውቀኝ በማውቀው ...
ስቃይ መከራዬን ከአንችው ዘንድ ያድርገው ። የሚለው
ጥላሁን ለኢትዮጵያ የነበረውን ፍቅር ከምንም በላይ የሚያሳይ ነው። ከባዕድ አገር ደስታ ይልቅ የሀገሩን መከራ የመረጠበት የሞቱ አጋጣሚ ደግሞ ለሀገሩ ያለውን ፍቅር በደሙ ያረጋገጠበት ታላቅ ክስተት ነው ።
ጥላሁን ከአሜሪካ ተነስቶ ለፋሲካ በዓል ወደ ሀገሩ መግባቱና በዚያው ዕለት ማረፉ፣ "በሀገሬ አፈር ልቀበር" የሚለውን ጥልቅ የኢትዮጵያዊያን ምኞት የፈጸመበት ነው ይህ ቀረኝ የማይል የሚያሰኘው እስከ መጨረሻው ትንፋሹ ድረስ ከሀገሩና ከሕዝቡ ጋር መቆየቱ ነው ።
ሲሞት መላው የአዲስ አበባ ሕዝብ በነቂስ ወጥቶ አስከሬኑን ሲሸኜው ጥላሁን ለሕዝቡ የሰጠውን ፍቅር ሕዝቡ በታላቅ ክብር የመለሰለት መሆኑን ቅድስት ስላሴ ቤተክርስቲያን ህያው ምስክር ናት ። ያ ለቅሶ የአንድ ድምፃዊ ስንብት ሳይሆን የኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጅና የልብ ትርታ ሽኝት ነበር።
ጥላሁን በሕይወቱና በሞቱ ሀገርን መውደድ ማለት ትርጉሙን እስከ ሞት ድረስ መታመንን አረጋግጦበታል።
ሰውን መውደድ ! አብሮ ማልቀስና መቆም ሙያን መውደድ እስከ መጨረሻዋ ትንፋሽ ድረስ መዘመር ለኢትዮጵያዊያን ከድምፃዊነት በላይ የአንድነት ምልክት መሆን ነው።
እኔ በዓይኔ ያየሁትን በልቤ የሰነድኩትን ይህንን ታሪክ ለሚቀጥለው ትውልድ ሊተላለፍ የሚገባው የፍቅርና የሀገር አምልኮ ትልቅ ትምህርት ይሆናል ብየ ሳዘጋጀው ጥላሁን ገሠሠ
ትንፋሼ ተቀርፆ ይቀመጥ ማልቀሻ ይህ ነው የሞትኩለት የኔ ማስታወሻ
ታሪኬ ነው ድምፄ በማለት ያንጎራጎረው ሙዚቃ ከፍቼ እያዳመጥኩ ነበር።
ይህ ስንኝ ጥላሁን ገሠሠ አስቀድሞ በድምፁ የህይወቱ ታሪክ የሞቱ ማስታወሻ እና የሀገሩ ውበት መገለጫ እንደሚሆን ተረድቶት የተጫወተው ነበር ማለት ይቻላል ። ጥላሁን በጥቁርና ነጭ ወረቀት ላይ የሰፈረ ኑዛዜ ሳይሆን የተውልን በህይወት ቆሞ በዜማ የተናዘዘው ድንቅ ስንብት ነበረ ።
እነዚህ ስንኞች የጥላሁንን የጥበብ ክብርና ትህትና ሲገለፅበት እያዳመጥኩት ነበር ይህን ታሪክ የፃፍኩት ።
ወዳጃቸ
የጥላሁን ገሠሠ ድምፅ ዝም ብሎ የአየር ንዝረት አይደለም፤ ማንነቱ፣ ታሪኩና ለሀገሩ የከፈለው መስዋዕትነት ነው። በጩኸት መኖሬን ማለቱ ለሀገርና ለፍቅር ሲል ድምፁን እስከ መጨረሻው የጥገታ ነጥብ ድረስ መጠቀሙንና ለዚህም መሞቱን ያሳያል።
ድምፄን ሰምቶ ያዝናል ለረገፈው አፅሜ ሲል
እጅግ ልብ ይነካል !
ጥላሁን በከፍታው ላይ ሆኖ እንኳ ያስቀየምኩት ቢኖር ብሎ ይቅርታን ይጠይቃል። የሞተውን አፅሙን ሳይሆን የቀረውን ድምፁን ሰምተው ሰዎች እንዲያዝኑለትና ይቅር እንዲሉት መመኘቱ የሰው ልጅነቱንይቅርታና ትህትናውን
ፍርጥ አድርጎ ያሳያል።
ጥላሁን ገሠሠ በድምፁና በህይወቱ የሰራው ትልቁ ስራ ፍቅርንና ኢትዮጵያዊነትን ማዳን ነበር። ጥላሁን ከቀላል ስሜትነት አልፎ ሕይወት መስዋዕትነትና የሀገር ፍቅር ጥግ መሆኑን በሚገባ አስገንዝቦናል።ጥበብ እንዴት የአንድን ሕዝብ ወኔና ማንነት እንደምትቀርፅ ጥላሁን ትልቅ ማሳያ ነው።
ፍቅር ተግባር ነው ፍቅር ዝም ብሎ የሚሰማን ስሜት ሳይሆን እንደ ጥላሁን ዜማዎች ራስን አሳልፎ እስከ መስጠት የሚደርስ ውሳኔ መሆኑን መረዳት ከባድ አይደለም ።
ጥላሁን ገሰሰ የሚዘፈነው ለጆሮ ብቻ ሳይሆን ለህሊና እና ለነፍስ ጭምር ይመስለኛል ።
ጥላሁን ዛሬ በሥጋ ቢለየንም ታሪኬ ነው ድምፄ ብሎ እንደተናዘዘው ሁሉ ዛሬም በየልባችን ውስጥ ንጉሥ ሆኖ ይኖራል።እሱ ለሀገር ብቻ ሳይሆን ለሰው ልጅ ስቃይ የሚራራ የህሊና ድምፅ ነበረው።
የሀገር ፍቅር ለአፈርና ለሰንደቅ ዓላማ የሚከፈል የአጥንትና የደም መስዋዕትነት ሲሆን ጥላሁን ገሠሠ በስጋ ቢለየንም ያ በሕይወት ያለ ሐውልት ግን በዜማዎቹ ውስጥ ሁሌም አዲስ ሆኖ ይኖራል።
ባጭሩ የጥላሁን መሞት ዝም ብሎ የአንድ ድምፃዊ ማለፍ ብቻ አልነበረም የአንድ ዘመን መቋጫ የአንድ ትልቅ ተስፋ መደብዘዝ እና በኢትዮጵያ ሰማይ ላይ የሚበራው የሙዚቃ ኮከብ ወድቆ ሲሰበር
ሰማይ ባዶ የሆነ ያህል ተሰምቶናል።
ጥላሁን ገሠሠ በደስታ ጊዜ አብሮን የሚጨፍር በጦርነት ጊዜ ፊታውራሪ ሆኖ የሚያዘምት በረሃብና በችግር ጊዜ ደግሞ አብሮን የሚላቀስ የሕዝብ ልብ ነበር ።
ጥላሁንን ከአቅም በላይ ያደረገው ይሄው ሁለንተናዊነቱ ነው። ለፍቅር ለሀገርና ለሰብአዊነት የነበረው ጽናት እሱ ሞቶም እንዲኖር አድርጎታል።
የጥላሁን ገሠሠ ዘፈኖች "ኢትዮጵያዊ ስነ-ሰብዕና" የሚባል የፍልስፍና ዘርፍ ቢኖር የዛ ዘርፍ ዋና መማሪያ መፅሐፍ ይሆኑ ነበር ።ብቻ
የጥላሁንገሰሰ ሕይወት ልክ እንደ አንድ የተቀደሰ መፅሐፍ በመሆኑ እራሡ ከፍቶ እራሱ ዘግቶት አልፏል ።
ለዚህ ታላቅ ድምፃዊ በተወለደበት ከተማ አዲስ አበባ ላይ ዘላለማዊ ምልክት ሆኖ እንዲቀመጥ ሐውልቱ ስለቆመለት ደስታዬ ወደር የለውም ።
ነፍስ ይማር !!
1 month ago
"CEO's" ምሽት!
አንጋፋ የኪነጥበብ ምሽት!
እባክዎ ሸር በማድረግ ተባበሩን!
54ኛው የባህል ማዕከል የኪነጥበብ ምሽት ረቡዕ ሚያዚያ 28፥2018 ዓ.ም ይካሄዳል።
በዕለቱም የምንጊዜም የኢትዮጵያዊያን ሆነ የአፍሪካ ኩራት የሆነው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ መስፍን ጣሰው የክብር እንግዳችን ሆነው በመካከላችን በመገኘት ሙያዊ ልምዳቸውን ያካፍሉናል።
እንዲሁም ግጥሞች ፣ ወግ ፣ ሙዚቃና ሞኖሎግ ለእናንተ ውድ ታዳሚዎቻችንን በባህል ማዕከል አዳራሽ ከቀኑ በ 11: 30 ጀምሮ ተሰናድቶ ይጠብቃችኃል።
#ማስታወሻ :—
ፕሮግራሙ ላይ ለመታደም የምትፈልጉ በአሁን ሰዓት የዩኒቨርስቲው ተማሪ ያልሆናችሁ የስነ-ጽሑፍ አፍቃሪያን መግቢያው በ5ተኛ በር በኩል ነው።
አንጋፋ የኪነጥበብ ምሽት!
እባክዎ ሸር በማድረግ ተባበሩን!
54ኛው የባህል ማዕከል የኪነጥበብ ምሽት ረቡዕ ሚያዚያ 28፥2018 ዓ.ም ይካሄዳል።
በዕለቱም የምንጊዜም የኢትዮጵያዊያን ሆነ የአፍሪካ ኩራት የሆነው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ መስፍን ጣሰው የክብር እንግዳችን ሆነው በመካከላችን በመገኘት ሙያዊ ልምዳቸውን ያካፍሉናል።
እንዲሁም ግጥሞች ፣ ወግ ፣ ሙዚቃና ሞኖሎግ ለእናንተ ውድ ታዳሚዎቻችንን በባህል ማዕከል አዳራሽ ከቀኑ በ 11: 30 ጀምሮ ተሰናድቶ ይጠብቃችኃል።
#ማስታወሻ :—
ፕሮግራሙ ላይ ለመታደም የምትፈልጉ በአሁን ሰዓት የዩኒቨርስቲው ተማሪ ያልሆናችሁ የስነ-ጽሑፍ አፍቃሪያን መግቢያው በ5ተኛ በር በኩል ነው።
1 month ago
አዲሱ የአራዳ ፓርክ የታሪክ ማስታወሻ የውበት ምንጭና የዘመናዊነት መገለጫ
#ethiopia | የአራዳ ፓርክ ቀደም ሲል የነበረውን የቆሻሻ የብክለትና የድህነት ገጽታ ሙሉ በሙሉ በመቀየር በአዲስ መልክ የተገነባ ታላቅ ፕሮጀክት ነው::
ይህ ስራ የቆዩ አሉታዊ የታሪክ አሻራዎችን በማጥፋት የኢትዮጵያን አዲስ ማንነትና ውበት ለትውልድ በሚተርክ መልኩ ተከናውኗል::
ከፒያሳ አካባቢ የለቀቁ ነዋሪዎች ለሰብአዊ ክብር ከማይመጥኑ ቤቶች ወጥተው መሰረተ ልማት ወደተሟላላቸው ዘመናዊ መኖሪያዎች እንዲገቡ ተደርጓል::
ነዋሪዎቹ ማህበራዊ ትስስራቸውን ሳይበጥሱ እድርና እቁባቸውን ጠብቀው እንዲኖሩ መደረጉም የልማቱ ልዩ ገጽታ ነው:: ፒያሳ ዳግም የተገነባችው እውነተኛ ስልጣኔን በሚያንጸባርቅ መልኩ ሲሆን በአካባቢው የነበሩ ወንዞችም ከቆሻሻ ጸድተው ለስራ እድል ፈጠራና ለቱሪስት መዳረሻነት እንዲውሉ ተደርገዋል::
በ40 ሄክታር መሬት ላይ ያረፈው የአራዳ ፓርክ የሚከተሉትን ዋና ዋና አገልግሎቶች ይዟል
የመንገድና የትራንስፖርት መሰረተ ልማት
5 ኪሎ ሜትር የአስፓልት መንገድ 6 ኪሎ ሜትር የእግረኛ መንገድ 5 ኪሎ ሜትር የብስክሌት መስመር እና 5 ኪሎ ሜትር የመሮጫ ትራክ ተገንብቶለታል::
የንግድና የፋይናንስ ዘርፍ
ከፒያሳ ለተነሱ ነጋዴዎች ቅድሚያ የሚሰጥባቸው 131 ዘመናዊ ሱቆች 7 ካፌና ሬስቶራንቶች አንድ ትልቅ ሱፐርማርኬት እና የባንክ ቅርንጫፍ ተካተዋል::
የመዝናኛና የስፖርት አገልግሎቶች
ዘመናዊ የአካል ብቃት ማእከል 7 አዳራሾች 8 ፕላዛዎች 3 አንፊ ቴአትሮች እና ማራኪ የሆነ ተንቀሳቃሽ ፏፏቴ ይገኛሉ:: በተጨማሪም 100 ሜትር ርዝመት ያለው የሀገሪቱ ረጅሙ የሰንደቅ ዓላማ መስቀያ በዚሁ ፓርክ ተተክሏል::
የህጻናትና ቤተሰብ ስፍራዎች
አራት ዘመናዊ የህጻናት መጫወቻዎች እና ህጻናት ስለ ሀገራቸው ግንዛቤ የሚያገኙበት ትንሿ ከተማ የተሰኘ ልዩ ስፍራ ተዘጋጅቷል::
የአረንጓዴ ልማትና የንጽህና አገልግሎት
15 ሄክታር መሬት በሳርና በተክሎች የተሸፈነ ሲሆን 22 የህዝብ መጸዳጃ ቤቶች እና 131 መኪናዎችን የሚይዝ ሰፊ ማቆሚያ ተገንብቷል::
ይህ ፕሮጀክት የመሬት አጠቃቀምን በብቃት ያረጋገጠ ሲሆን ከመሬት በታች ለሱቆችና ለአዳራሾች ከላይ ደግሞ ለፕላዛ አገልግሎት እንዲውል ተደርጓል::
እንዲሁም በአካባቢው የነበሩ ከ700 በላይ ታሪካዊ ቤቶችና ህንጻዎች ይዘታቸውን ሳይለቁ እንዲታደሱ ተደርጓል::
በአጠቃላይ ፓርኩ ከንግድ እስከ ስፖርት እንዲሁም ከቤተሰብ መዝናኛ እስከ ስነ ጥበብ መድረኮችን የያዘ የከተማዋ አዲስ የቱሪስት መስህብ ነው::
#aradapark #piassa #addisababacity #urbandevelopment #greenlegacy #tourismethiopia #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | የአራዳ ፓርክ ቀደም ሲል የነበረውን የቆሻሻ የብክለትና የድህነት ገጽታ ሙሉ በሙሉ በመቀየር በአዲስ መልክ የተገነባ ታላቅ ፕሮጀክት ነው::
ይህ ስራ የቆዩ አሉታዊ የታሪክ አሻራዎችን በማጥፋት የኢትዮጵያን አዲስ ማንነትና ውበት ለትውልድ በሚተርክ መልኩ ተከናውኗል::
ከፒያሳ አካባቢ የለቀቁ ነዋሪዎች ለሰብአዊ ክብር ከማይመጥኑ ቤቶች ወጥተው መሰረተ ልማት ወደተሟላላቸው ዘመናዊ መኖሪያዎች እንዲገቡ ተደርጓል::
ነዋሪዎቹ ማህበራዊ ትስስራቸውን ሳይበጥሱ እድርና እቁባቸውን ጠብቀው እንዲኖሩ መደረጉም የልማቱ ልዩ ገጽታ ነው:: ፒያሳ ዳግም የተገነባችው እውነተኛ ስልጣኔን በሚያንጸባርቅ መልኩ ሲሆን በአካባቢው የነበሩ ወንዞችም ከቆሻሻ ጸድተው ለስራ እድል ፈጠራና ለቱሪስት መዳረሻነት እንዲውሉ ተደርገዋል::
በ40 ሄክታር መሬት ላይ ያረፈው የአራዳ ፓርክ የሚከተሉትን ዋና ዋና አገልግሎቶች ይዟል
የመንገድና የትራንስፖርት መሰረተ ልማት
5 ኪሎ ሜትር የአስፓልት መንገድ 6 ኪሎ ሜትር የእግረኛ መንገድ 5 ኪሎ ሜትር የብስክሌት መስመር እና 5 ኪሎ ሜትር የመሮጫ ትራክ ተገንብቶለታል::
የንግድና የፋይናንስ ዘርፍ
ከፒያሳ ለተነሱ ነጋዴዎች ቅድሚያ የሚሰጥባቸው 131 ዘመናዊ ሱቆች 7 ካፌና ሬስቶራንቶች አንድ ትልቅ ሱፐርማርኬት እና የባንክ ቅርንጫፍ ተካተዋል::
የመዝናኛና የስፖርት አገልግሎቶች
ዘመናዊ የአካል ብቃት ማእከል 7 አዳራሾች 8 ፕላዛዎች 3 አንፊ ቴአትሮች እና ማራኪ የሆነ ተንቀሳቃሽ ፏፏቴ ይገኛሉ:: በተጨማሪም 100 ሜትር ርዝመት ያለው የሀገሪቱ ረጅሙ የሰንደቅ ዓላማ መስቀያ በዚሁ ፓርክ ተተክሏል::
የህጻናትና ቤተሰብ ስፍራዎች
አራት ዘመናዊ የህጻናት መጫወቻዎች እና ህጻናት ስለ ሀገራቸው ግንዛቤ የሚያገኙበት ትንሿ ከተማ የተሰኘ ልዩ ስፍራ ተዘጋጅቷል::
የአረንጓዴ ልማትና የንጽህና አገልግሎት
15 ሄክታር መሬት በሳርና በተክሎች የተሸፈነ ሲሆን 22 የህዝብ መጸዳጃ ቤቶች እና 131 መኪናዎችን የሚይዝ ሰፊ ማቆሚያ ተገንብቷል::
ይህ ፕሮጀክት የመሬት አጠቃቀምን በብቃት ያረጋገጠ ሲሆን ከመሬት በታች ለሱቆችና ለአዳራሾች ከላይ ደግሞ ለፕላዛ አገልግሎት እንዲውል ተደርጓል::
እንዲሁም በአካባቢው የነበሩ ከ700 በላይ ታሪካዊ ቤቶችና ህንጻዎች ይዘታቸውን ሳይለቁ እንዲታደሱ ተደርጓል::
በአጠቃላይ ፓርኩ ከንግድ እስከ ስፖርት እንዲሁም ከቤተሰብ መዝናኛ እስከ ስነ ጥበብ መድረኮችን የያዘ የከተማዋ አዲስ የቱሪስት መስህብ ነው::
#aradapark #piassa #addisababacity #urbandevelopment #greenlegacy #tourismethiopia #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
1 month ago
Abebe Tilahun culture & Sport:
ለፈረንጅ ሚስቶች የቆመች ሐውልት‼️
የመጽሐፉ ርዕስ፦ የፈረንጅ ሚስት
ደራሲት፦ እስከዳር ግርማይ
የገጽ ብዛት ፦ 119
የመጽሐፉ ዋጋ ፦ 150 ብር
እትም፦ 3ኛ /2017 ዓ.ም
ዘውግ፦ ግለ ማስታወሻ (Memoir)+
አርታኢያን፦ ደራሲ ኃይለመለኮት መዋዕል እና አርቲስት አዜብ ወርቁ
👉መንደርደሪያ
ካርል ሮጀርስ (Carl Rogers) የተባለው ታዋቂው አሜሪካዊ የሥነ-ልቦና ባለሙያ "On Becoming a Person" በተሰኘ መጽሐፉ ላይ በሰዎች መካከል ያለውን ጥልቅ ግንኙነት በማጥናት እንዲህ ይላል። “What is most personal is most universal.” ፦ “እጅግ ሲበዛ ግላዊ የሆነው ነገር፣ እጅግ ሲበዛ ዓለማቀፋዊ ነው።”
ግለ-ማስታወሻ (Memoir)፤ ከሕይወት ውስጥ አንድን ወሳኝ ክስተት፣ ስሜት ወይም ጭብጥ (Theme) መርጦ ይተነትናል። ትኩረቱ "ከገጠመኝ ነገር ምን ተማርኩ? ምን ተሰማኝ?" የሚል ነው። በሌላ አነጋገር ግለ-ማስታወሻ ከታሪክ ይልቅ ትርጓሜና ስሜት ላይ ያተኩራል።
አንድ ሰው ለብቻው የሚሰማው፣ ለሌላ ሰው ለመናገር የሚፈራው ወይም "እኔ ብቻ ነኝ እንዲህ የሚሰማኝ" ብሎ የሚያስበው የግል ስሜት (ለምሳሌ፦ የፍርሃት፣ የብቸኝነት ስሜት፣ ወይም የናፍቆት፣ የመበሳጨትና የመብከንከን ስሜት) በሚገርም ሁኔታ ሌሎች ሰዎችም በውስጣቸው የሚሰማቸው ነው።
ስለሆነም ጸሐፊዋ እስከዳር ስለ ራሷና በዙሪያዋ ስላሉ ተመሳሳይ ሰዎች እጅግ ጥብቅና ግላዊ የሆኑ ጉዳዮችን በሐቀኝነት ስትናገር፣ በዓለም ዙሪያ ያሉ ሰዎች በታሪኳ ውስጥ የራሳቸውን ስሜት አግኝተውታል። የሥነ-ልቦና ጠበብት አንድ ሰው ወደ ራሱ ማንነት (Inner self) በጥልቀት በወረደ ቁጥር፣ ከግል ማንነቱ ባለፈ የሰው ልጅን የጋራ ማንነት (Collective Human Experience) ያገኛል ብለው ያምናሉና በፈረንጅ ሚስት የሆነውም ይሄው ነው።
ሌላኛው ጄምስ ጆይስ (James Joyce)የተባለ ምሁር "በተለየው (in the particular) ውስጥ ሁልጊዜም ዓለማቀፋዊውን (the universal) ነገር እናገኛለን።" በማለት በሥነ-ጽሑፍ ሥራዎቹ የግል ተሞክሮን ማዕከል ማድረጉን ገልጿል። እንዲሁም ራልፍ ዋልዶ ኤመርሰን (Ralph Waldo Emerson) "በገዛ ልብህ ውስጥ የምታምነው እውነት ለሁሉም ሰዎች እውነት ነው።" በሚል ሀሳብ ተመሳሳይ ፍልስፍናን አራምዷል።
በአጠቃላይ አባባሉ "የሰው ልጅ ስሜትና ተፈጥሮ በየትኛውም ቦታ አንድ ነው" የሚለውን መሠረታዊ እውነት የሚያሳይ ነው። የፈረንጅ ሚስት የሚለው ግለ-ማስታወሻ በራስ ሕይወት መስኮትነት ዓለምን የማሳያ ጥበብ ሆኖ ብቅ ብሏል። ጸሐፊዋ በራሷ ሕይወት ውስጥ ያለውን ትርጉም ስትፈልግ፣ አንባቢው ደግሞ በጸሐፊው ታሪክ ውስጥ የራሱንና የማኅበረሰቡን ሕይወት ያያል፣ ይታዘባል።
የፈረንጅ ሚስት
👉ግላዊና ዓለማቀፋዊ ሀሳብ፤ ጸሐፊዋ ስለ ራሷ ብቻ ስታወራ ለአንባቢው አሰልቺ ሊሆን ይችላል። ነገር ግን በግል ሕይወቷ በፈረንጅ ሚስትነቷ፣ በኢትዮጵያዊነቷ፣ የደረሰባትን ሐዘን፣ ፍቅር፣ ክህደት ወይም መገለል በሐቀኝነት ስለገለጠችው፣ አንባቢያን በራሳቸው ሕይወት ውስጥ ተመሳሳይ ስሜት አጋጥሟቸው ስለሚያውቅ ከጸሐፊዋ ጋር፣ እንደግል በሀሳብ፣ እንደማኅበረሰብ በአባልነት ይቆራኛሉ።
ሰው ወደ ራሱ ውስጠት በጥልቀት በቆፈረ ቁጥር፣ የሁሉንም ሰው የጋራ ምንጭ ያገኛል። የራስን እውነተኛ ስሜት፣ ስቃይ እና ደስታ መፈለግ እና እዚያ ጥልቀት ላይ ሲደርሱ የምናገኘው ራስን ብቻ ሳይሆን መላውን የሰው ልጅ የሚያገናኘውን የጋራ ክር ነው። ለዚህ ነው ግላዊ ማስታወሻዎች (Memoirs) በሚገባ ተቆፍረው ሲጻፉ ዓለምን ሁሉ የመንካት አቅም የሚኖራቸው።
በሥነ-ጽሑፍ እና በፈጠራ ድርሰት ዓለም ውስጥ በስፋት የምትታወቀው አሜሪካዊት ጸሐፊ ማያ አንጄሉ (Maya Angelou) “In the particular is contained the universal.” ፦ በተለየው/በግል ታሪክ ውስጥ፣ ዓለማቀፋዊው እውነት ይገኛል። ብላለች ።
ይህች የፈረንጅ ሚስት መጽሐፍ ከኢትዮጵያዊ ወንድ ውጭ ላገባችሁ ቀወል ስም የፈረንጅ ሚስት ለምትባሉ ሁሉ ሴቶች የቆመች ቅልብጭ ያለች ሐውልት ናት።
👉በፈረንጅ ሚስት መጽሐፍ ውስጥ ፤
ሐቀኝነት (Honesty)አለ፦ ግለ-ማስታወሻ ጸሐፊዋ ራሷን ብቻ ያሞግሰችበት ሳይሆን፣ ድክመትና ስህተቶችንም ጭምር የገለጥችበት መጽሐፍ ነው። ሐቀኝነት ከሌለ አንባቢው በታሪኩ አይመሰጥም።
የራስ መተማመኗን ፈረንጅ የማግባት ውጤት ሲያደርጉት፤ ሐበሻ ብታገባ ኖሮ በዚህ የራስ መተማመኗ ድሮ እንደሚፈታት ሲያሙላት በስላቅ ሐቋን ትጠይቃለች።
"እውነት የሀገሬ ሴቶች ታዋቂ፣ ተጽዕኖ ፈጣሪ እና በራሳችሁ
የምትተማመኑ ከሆናችሁ ትዳራችሁ አይጸናም?
ደመወዛችሁ ከባለቤታችሁ ደመወዝ ሲበልጥ፣ ሥልጣናችሁ ከትዳራችሁ በላይ ሲገዝፍ ትፋታላችሁ?
ወይስ ትዳራችሁን መርጣችሁ፣ የመጣላችሁን ዕድል አሳልፋችሁ ለወንድ እና ላላገቡ ሴቶች ትሰጣላችሁ?
የሀገሬ ወንዶችስ? በሥራ፣ በደመወዝ ወይም በሥልጣን የምትበልጣችሁን ሴት ማግባት ትፈራላችሁ እንዴ?"
መልስ አትፈልግም።
ይልቁንስ ደራሲዋ ጥያቄዎቹን የምታቀርበው ምላሽ ፈልጋ ሳይሆን፣ ማኅበረሰቡን በመስታወት ፊት አቁማ ራሱን እንዲታዘብ ለማድረግ ነው።
ጭብጥ (Theme)አለ፦ ታሪኳ የሚሽከረከርበት አንድ ማዕከላዊ እውነት አለው ። ማዕከላዊ እውነቷ በማኅበረሰባችን ዘንድ ለፈረንጅ ሚስት ያለውን ስሁት አመለካከት ማረም፣ እውነቷንና ጽናቷን በመግለጽ ማንነቷን ማሳየት ነው። ለእያንዳንዱ ገጠመኟ በተግባር የተፈጸመ ምሳሌ ያልደበዘዘ ትውስታ ተቀምጧል ።
በማኅበረሰባችን ዘንድ የፈረንጅ ሚስትን ከሚያራክስበት ዝቅጠታዊ ልማድ የባሰ የሀብታም ቅምጥን የሚያሞግስበትና የሚያከብርበት የስብእና ንጥፈት እንዴት እንዳብከነከናት በሚቆጠቁጥ መልኩ የማዕከላዊ ጭብጡ ማጠንጠኛ ሆኗል ።
ደሞ ለምን ፈረንጅ አገባሽ ? እያሉ የጅል ጥያቄ ለሚጠይቁ አድርቅ ጋዜጠኞች ጥያቄን በጥያቄ በመመለስ በጥያቄያቸው እንዲያፍሩ የምታደርግበት ጥበብ የፈረንጁ ባሏ ምክርና የጭብጧ ማጠናከሪያ ነበር።
"ባለቤቴ ሁል ጊዜ የማይደረስ ጥያቄ ለሚጠይቅሽ ሰው፤ የጠየቀሽን ጥያቄ መልሰሽ ራሱን ጠይቂው። መልሱ ካላጠገበሽ ምን ማለትህ ነው? ብለሽ ይበልጥ እንዲያብራራልሽ እንደገና ጠይቂው። ስህተቱን
እስኪረዳው ተፋተኚው። እንደዚህ ዐይነት ሰዎች ከአምስት
ጥያቄዎች በላይ መመለስ አይችሉም፤ የሚለኝን ሳስበው ተግባራዊ እያደረግኩ።" ትለናለች። (ገጽ34)
ጥበባዊ አቀራረብ አለ፦ ምንም እንኳን እውነተኛ ታሪክ ቢሆንም፣ እንደ ልብ-ወለድ (Fiction) የታሪክ አወቃቀር፣ ገጸ-ባህሪያት አሳሳል እና የቃላት ምርጫ (Imagery) ተጠቀማለች። እንደ ገጸ ባሕርይ ራሷን እና በዙሪያዋ ያሉ ተመሳሳይ ሕይወት የሚጋሩ ወዳጆቿን፣ ቤተሰቦቿን እና በመንገዷ የገጠሟትን አካታለች። የታሪክ አወቃቀሩ ከአንዱ የሕይወት ገጠመኝ ወደ ሌላኛው የሕይወት ገጠመኝ እየተሻገረች፣ በትውስታ እያጀበች በምሳሌ አዋቅራ የልቧን እውነት የሕይወቷን ትርክት ቀንጭባ አቅርባዋለች።
የቃላት አመራረጧ ትኩሳቷን በመግለጥ እንደ እሳት የሚጋረፉ ፣ ስታዝን የሚለዝቡ፣ ስትቆጣ የሚንጣጡ ቃላት ናቸው።
ለምሳሌ የሀብታም ቅምጥን የገለጠችበትን ቃላት ተመልከቱ፦ "የሀብታም ቅምጥ የከተማው ሁሉ ወንድ የሚመኛት፣ ያሳደጓት የሰፈር ጎረምሶች ዓይናቸው እያየ ለባለጸጋ አሳልፈው በመስጠታቸው የሚቆጩባት፣ ዘመድ አዝማዶቿ የእሷ ስኬት የልጆቻቸው ባለመሆኑ የሚቀኑባት፣ የሰፈሩ ሰዎች ለአቅመ ሔዋን ላልደረሱ ልጆቻቸው "አርአያነቷን" እንዲከተሉ ጀብዳቸውን የሚነግሩላት፤ በየቦታው ትንሽዬ "ፈጣሪ" ሆና ብዙ "ደቀ መዛሙርት" ያፈራች ሴት ናት።" (ገጽ 27)
ውስጣዊ ሙግት (Internal Dialogue/ አለ፦ በሆነባት በተደረገባት ነገር ብቻ ሳይሆን፤ የወጣችበት ማኅበረሰብ ግንዛቤ ባለበት ቆሞ መቅረት ጭምር ሲያብሰከስካት ፤ እንደግል መብቷን፣ እንደማኅበረሰብ ውበቷን ስትገፈፍ የምትናገራቸው ቃላት የውስጧን መብከንከን ይገልጻሉ።
"የማዝነው፤ ማኅበረሰባችን በየመንገዱ መሰደቧን እንዳላየ እንዳልሰማ ሆኖ ስለሚያልፋት ብቻ አይደለም ። ከሐበሻ ወንድ ወጭ ሲሆን በፍቅር የማትወድቅ፣ ከሀገሯ ቋንቋ በቀር የፍቅር ቃላት የማትሰማ፣ ጠረን ለምዳ የማትሸነፍ ናት፤ ብለው በመወሰናቸውና የስሜት ሕዋሳቷ ለሌላ ሀገር ዜጋም ቢሆን እንደሚሠሩ ባለማወቃቸውም እንጂ!" (ገጽ16)
"ውጭ ሀገር ስንኖር አለመከበራችን በምንም መልኩ ልክ አይደለም፤ በሰው ሀገር ስንከፋ የሚሰማን ስሜት ፣ ከራሳችን ሀገር ከሚደርስብን የጥቃት ስሜት ጋር ካነጻጸርነው ግን፣ የሕመሙ ክብደት በሰው ሀገር
ሲሆን ይቀንሳል።
ሀገር ያስከፋን ጊዜ ግን ወዴት አቤት ይባላል? የራስ ሕዝብስ ለማን ይከሰሳል?" እያለች ምሯን ትናገራለች።
እናቴ አሳዛኝና አንጀት ቆራጭ ነገሮች ሲገጥሟት፦ "ከቀላድም ባይረዝም ከመጫኛም ባይበልጥ፤
አንጀት ያልቅ የለም ወይ ሲቆረጥ ሲቆረጥ።" ትላለች ።
የማኅበረሰባዊ መገፋት አንጀት ይቆርጣል ፤ አይመልሰኝ አሰኝቶ ድንጋይ ያስወረውራል። በጊዜ ሊታረም ከዘመኑ ጋርም ሊዘምን የሚገባ እንጅ የምናጌጥበት ነውር መሆን የለበትም ።
👉በፈረንጅ ሚስት መጽሐፍ
ደራሲዋ እስከዳር ግርማይና መሰል የፈረንጅ ሚስቶች ያለፈና ያለን ቁስል በቃላት አስጊጣ በመግለጧ ግላዊ እፎይታ ፣ ሕሊናዊ ፈውስ አግኝተውበታል፤ ብዬ ተስፋ አደርጋለሁ ።
በመሰል ፈተና ውስጥ ያሉ ሰዎች የግለ ማስታወሻዎቹን ሂደትና መፍትሔ አይተው ተስፋ የሚሰጥ ትምህርት ያገኛሉ። በማኅበረሰባዊ ሂሷም ብዙዎች ራሳቸውን እንዲታዘቡ ራሳቸውን እንዲመረምሩና እንዲታረሙ ኮርኩራለች።
እስከዳር በራሷ የተወሰነ ዘመንና ማኅበረሰብ ውስጥ ለፈረንጅ ሚስት የነበረን አመለካከት ለትውልድ በማስተላለፍ የታሪክ ምስክር በመሆን፤ ለፈረንጅ ሚስቶች ሐውልት አቁማለች።
ማጠቃለያ
ደራሲ እስከዳር ግርማይ በመጽሐፏ ውስጥ 'የፈረንጅ ሚስት' የሚለውን ስም ከስድብነት ወደ ማንነት (Identity)፣ ከማንነትም ወደ ተጋድሎ (Resistance) ቀይራዋለች። ይህ መጽሐፍ የአንድን ግለሰብ ሕይወት ብቻ ሳይሆን፣ የኢትዮጵያዊነትን እና የዘመናዊነትን (Modernity) ግጭት፣ እንዲሁም የሴትነትን ነፃነት የሚፈትን፣ ማኅበረሰባዊ ሕጸፅን ነቅሶ የሚያሳይ መስታወት ነው።
👉እስከዬ አሁንም ያላወጣሽው ብዙ ግላዊ "የመሬማውያን ጉዳይ" አለና በጥልቀት ቆፍረሽ ታወጭው ዘንድ አደራ እላለሁ 🙏
👉የፈረንጅ ሚስት በዶክመንተሪ ቢዘጋጅ ደግሞ ከንባብ የራቀውና የስድብ መጋዘን ከሆነው የማኅበረሰብ ክፍል ውስጥ በእጁ ላይ ገብተሽ ትነግሪዋለሽ። የፈረንጅ ሚስት ማለት በምን የሕይወት ሸለቆ ውስጥ አልፋ ምርጫዋን የምታስከብር እንደሆነች ታሳያቸዋለሽ።
የሀብከ ብርሃኔ ጥላሁን
ለፈረንጅ ሚስቶች የቆመች ሐውልት‼️
የመጽሐፉ ርዕስ፦ የፈረንጅ ሚስት
ደራሲት፦ እስከዳር ግርማይ
የገጽ ብዛት ፦ 119
የመጽሐፉ ዋጋ ፦ 150 ብር
እትም፦ 3ኛ /2017 ዓ.ም
ዘውግ፦ ግለ ማስታወሻ (Memoir)+
አርታኢያን፦ ደራሲ ኃይለመለኮት መዋዕል እና አርቲስት አዜብ ወርቁ
👉መንደርደሪያ
ካርል ሮጀርስ (Carl Rogers) የተባለው ታዋቂው አሜሪካዊ የሥነ-ልቦና ባለሙያ "On Becoming a Person" በተሰኘ መጽሐፉ ላይ በሰዎች መካከል ያለውን ጥልቅ ግንኙነት በማጥናት እንዲህ ይላል። “What is most personal is most universal.” ፦ “እጅግ ሲበዛ ግላዊ የሆነው ነገር፣ እጅግ ሲበዛ ዓለማቀፋዊ ነው።”
ግለ-ማስታወሻ (Memoir)፤ ከሕይወት ውስጥ አንድን ወሳኝ ክስተት፣ ስሜት ወይም ጭብጥ (Theme) መርጦ ይተነትናል። ትኩረቱ "ከገጠመኝ ነገር ምን ተማርኩ? ምን ተሰማኝ?" የሚል ነው። በሌላ አነጋገር ግለ-ማስታወሻ ከታሪክ ይልቅ ትርጓሜና ስሜት ላይ ያተኩራል።
አንድ ሰው ለብቻው የሚሰማው፣ ለሌላ ሰው ለመናገር የሚፈራው ወይም "እኔ ብቻ ነኝ እንዲህ የሚሰማኝ" ብሎ የሚያስበው የግል ስሜት (ለምሳሌ፦ የፍርሃት፣ የብቸኝነት ስሜት፣ ወይም የናፍቆት፣ የመበሳጨትና የመብከንከን ስሜት) በሚገርም ሁኔታ ሌሎች ሰዎችም በውስጣቸው የሚሰማቸው ነው።
ስለሆነም ጸሐፊዋ እስከዳር ስለ ራሷና በዙሪያዋ ስላሉ ተመሳሳይ ሰዎች እጅግ ጥብቅና ግላዊ የሆኑ ጉዳዮችን በሐቀኝነት ስትናገር፣ በዓለም ዙሪያ ያሉ ሰዎች በታሪኳ ውስጥ የራሳቸውን ስሜት አግኝተውታል። የሥነ-ልቦና ጠበብት አንድ ሰው ወደ ራሱ ማንነት (Inner self) በጥልቀት በወረደ ቁጥር፣ ከግል ማንነቱ ባለፈ የሰው ልጅን የጋራ ማንነት (Collective Human Experience) ያገኛል ብለው ያምናሉና በፈረንጅ ሚስት የሆነውም ይሄው ነው።
ሌላኛው ጄምስ ጆይስ (James Joyce)የተባለ ምሁር "በተለየው (in the particular) ውስጥ ሁልጊዜም ዓለማቀፋዊውን (the universal) ነገር እናገኛለን።" በማለት በሥነ-ጽሑፍ ሥራዎቹ የግል ተሞክሮን ማዕከል ማድረጉን ገልጿል። እንዲሁም ራልፍ ዋልዶ ኤመርሰን (Ralph Waldo Emerson) "በገዛ ልብህ ውስጥ የምታምነው እውነት ለሁሉም ሰዎች እውነት ነው።" በሚል ሀሳብ ተመሳሳይ ፍልስፍናን አራምዷል።
በአጠቃላይ አባባሉ "የሰው ልጅ ስሜትና ተፈጥሮ በየትኛውም ቦታ አንድ ነው" የሚለውን መሠረታዊ እውነት የሚያሳይ ነው። የፈረንጅ ሚስት የሚለው ግለ-ማስታወሻ በራስ ሕይወት መስኮትነት ዓለምን የማሳያ ጥበብ ሆኖ ብቅ ብሏል። ጸሐፊዋ በራሷ ሕይወት ውስጥ ያለውን ትርጉም ስትፈልግ፣ አንባቢው ደግሞ በጸሐፊው ታሪክ ውስጥ የራሱንና የማኅበረሰቡን ሕይወት ያያል፣ ይታዘባል።
የፈረንጅ ሚስት
👉ግላዊና ዓለማቀፋዊ ሀሳብ፤ ጸሐፊዋ ስለ ራሷ ብቻ ስታወራ ለአንባቢው አሰልቺ ሊሆን ይችላል። ነገር ግን በግል ሕይወቷ በፈረንጅ ሚስትነቷ፣ በኢትዮጵያዊነቷ፣ የደረሰባትን ሐዘን፣ ፍቅር፣ ክህደት ወይም መገለል በሐቀኝነት ስለገለጠችው፣ አንባቢያን በራሳቸው ሕይወት ውስጥ ተመሳሳይ ስሜት አጋጥሟቸው ስለሚያውቅ ከጸሐፊዋ ጋር፣ እንደግል በሀሳብ፣ እንደማኅበረሰብ በአባልነት ይቆራኛሉ።
ሰው ወደ ራሱ ውስጠት በጥልቀት በቆፈረ ቁጥር፣ የሁሉንም ሰው የጋራ ምንጭ ያገኛል። የራስን እውነተኛ ስሜት፣ ስቃይ እና ደስታ መፈለግ እና እዚያ ጥልቀት ላይ ሲደርሱ የምናገኘው ራስን ብቻ ሳይሆን መላውን የሰው ልጅ የሚያገናኘውን የጋራ ክር ነው። ለዚህ ነው ግላዊ ማስታወሻዎች (Memoirs) በሚገባ ተቆፍረው ሲጻፉ ዓለምን ሁሉ የመንካት አቅም የሚኖራቸው።
በሥነ-ጽሑፍ እና በፈጠራ ድርሰት ዓለም ውስጥ በስፋት የምትታወቀው አሜሪካዊት ጸሐፊ ማያ አንጄሉ (Maya Angelou) “In the particular is contained the universal.” ፦ በተለየው/በግል ታሪክ ውስጥ፣ ዓለማቀፋዊው እውነት ይገኛል። ብላለች ።
ይህች የፈረንጅ ሚስት መጽሐፍ ከኢትዮጵያዊ ወንድ ውጭ ላገባችሁ ቀወል ስም የፈረንጅ ሚስት ለምትባሉ ሁሉ ሴቶች የቆመች ቅልብጭ ያለች ሐውልት ናት።
👉በፈረንጅ ሚስት መጽሐፍ ውስጥ ፤
ሐቀኝነት (Honesty)አለ፦ ግለ-ማስታወሻ ጸሐፊዋ ራሷን ብቻ ያሞግሰችበት ሳይሆን፣ ድክመትና ስህተቶችንም ጭምር የገለጥችበት መጽሐፍ ነው። ሐቀኝነት ከሌለ አንባቢው በታሪኩ አይመሰጥም።
የራስ መተማመኗን ፈረንጅ የማግባት ውጤት ሲያደርጉት፤ ሐበሻ ብታገባ ኖሮ በዚህ የራስ መተማመኗ ድሮ እንደሚፈታት ሲያሙላት በስላቅ ሐቋን ትጠይቃለች።
"እውነት የሀገሬ ሴቶች ታዋቂ፣ ተጽዕኖ ፈጣሪ እና በራሳችሁ
የምትተማመኑ ከሆናችሁ ትዳራችሁ አይጸናም?
ደመወዛችሁ ከባለቤታችሁ ደመወዝ ሲበልጥ፣ ሥልጣናችሁ ከትዳራችሁ በላይ ሲገዝፍ ትፋታላችሁ?
ወይስ ትዳራችሁን መርጣችሁ፣ የመጣላችሁን ዕድል አሳልፋችሁ ለወንድ እና ላላገቡ ሴቶች ትሰጣላችሁ?
የሀገሬ ወንዶችስ? በሥራ፣ በደመወዝ ወይም በሥልጣን የምትበልጣችሁን ሴት ማግባት ትፈራላችሁ እንዴ?"
መልስ አትፈልግም።
ይልቁንስ ደራሲዋ ጥያቄዎቹን የምታቀርበው ምላሽ ፈልጋ ሳይሆን፣ ማኅበረሰቡን በመስታወት ፊት አቁማ ራሱን እንዲታዘብ ለማድረግ ነው።
ጭብጥ (Theme)አለ፦ ታሪኳ የሚሽከረከርበት አንድ ማዕከላዊ እውነት አለው ። ማዕከላዊ እውነቷ በማኅበረሰባችን ዘንድ ለፈረንጅ ሚስት ያለውን ስሁት አመለካከት ማረም፣ እውነቷንና ጽናቷን በመግለጽ ማንነቷን ማሳየት ነው። ለእያንዳንዱ ገጠመኟ በተግባር የተፈጸመ ምሳሌ ያልደበዘዘ ትውስታ ተቀምጧል ።
በማኅበረሰባችን ዘንድ የፈረንጅ ሚስትን ከሚያራክስበት ዝቅጠታዊ ልማድ የባሰ የሀብታም ቅምጥን የሚያሞግስበትና የሚያከብርበት የስብእና ንጥፈት እንዴት እንዳብከነከናት በሚቆጠቁጥ መልኩ የማዕከላዊ ጭብጡ ማጠንጠኛ ሆኗል ።
ደሞ ለምን ፈረንጅ አገባሽ ? እያሉ የጅል ጥያቄ ለሚጠይቁ አድርቅ ጋዜጠኞች ጥያቄን በጥያቄ በመመለስ በጥያቄያቸው እንዲያፍሩ የምታደርግበት ጥበብ የፈረንጁ ባሏ ምክርና የጭብጧ ማጠናከሪያ ነበር።
"ባለቤቴ ሁል ጊዜ የማይደረስ ጥያቄ ለሚጠይቅሽ ሰው፤ የጠየቀሽን ጥያቄ መልሰሽ ራሱን ጠይቂው። መልሱ ካላጠገበሽ ምን ማለትህ ነው? ብለሽ ይበልጥ እንዲያብራራልሽ እንደገና ጠይቂው። ስህተቱን
እስኪረዳው ተፋተኚው። እንደዚህ ዐይነት ሰዎች ከአምስት
ጥያቄዎች በላይ መመለስ አይችሉም፤ የሚለኝን ሳስበው ተግባራዊ እያደረግኩ።" ትለናለች። (ገጽ34)
ጥበባዊ አቀራረብ አለ፦ ምንም እንኳን እውነተኛ ታሪክ ቢሆንም፣ እንደ ልብ-ወለድ (Fiction) የታሪክ አወቃቀር፣ ገጸ-ባህሪያት አሳሳል እና የቃላት ምርጫ (Imagery) ተጠቀማለች። እንደ ገጸ ባሕርይ ራሷን እና በዙሪያዋ ያሉ ተመሳሳይ ሕይወት የሚጋሩ ወዳጆቿን፣ ቤተሰቦቿን እና በመንገዷ የገጠሟትን አካታለች። የታሪክ አወቃቀሩ ከአንዱ የሕይወት ገጠመኝ ወደ ሌላኛው የሕይወት ገጠመኝ እየተሻገረች፣ በትውስታ እያጀበች በምሳሌ አዋቅራ የልቧን እውነት የሕይወቷን ትርክት ቀንጭባ አቅርባዋለች።
የቃላት አመራረጧ ትኩሳቷን በመግለጥ እንደ እሳት የሚጋረፉ ፣ ስታዝን የሚለዝቡ፣ ስትቆጣ የሚንጣጡ ቃላት ናቸው።
ለምሳሌ የሀብታም ቅምጥን የገለጠችበትን ቃላት ተመልከቱ፦ "የሀብታም ቅምጥ የከተማው ሁሉ ወንድ የሚመኛት፣ ያሳደጓት የሰፈር ጎረምሶች ዓይናቸው እያየ ለባለጸጋ አሳልፈው በመስጠታቸው የሚቆጩባት፣ ዘመድ አዝማዶቿ የእሷ ስኬት የልጆቻቸው ባለመሆኑ የሚቀኑባት፣ የሰፈሩ ሰዎች ለአቅመ ሔዋን ላልደረሱ ልጆቻቸው "አርአያነቷን" እንዲከተሉ ጀብዳቸውን የሚነግሩላት፤ በየቦታው ትንሽዬ "ፈጣሪ" ሆና ብዙ "ደቀ መዛሙርት" ያፈራች ሴት ናት።" (ገጽ 27)
ውስጣዊ ሙግት (Internal Dialogue/ አለ፦ በሆነባት በተደረገባት ነገር ብቻ ሳይሆን፤ የወጣችበት ማኅበረሰብ ግንዛቤ ባለበት ቆሞ መቅረት ጭምር ሲያብሰከስካት ፤ እንደግል መብቷን፣ እንደማኅበረሰብ ውበቷን ስትገፈፍ የምትናገራቸው ቃላት የውስጧን መብከንከን ይገልጻሉ።
"የማዝነው፤ ማኅበረሰባችን በየመንገዱ መሰደቧን እንዳላየ እንዳልሰማ ሆኖ ስለሚያልፋት ብቻ አይደለም ። ከሐበሻ ወንድ ወጭ ሲሆን በፍቅር የማትወድቅ፣ ከሀገሯ ቋንቋ በቀር የፍቅር ቃላት የማትሰማ፣ ጠረን ለምዳ የማትሸነፍ ናት፤ ብለው በመወሰናቸውና የስሜት ሕዋሳቷ ለሌላ ሀገር ዜጋም ቢሆን እንደሚሠሩ ባለማወቃቸውም እንጂ!" (ገጽ16)
"ውጭ ሀገር ስንኖር አለመከበራችን በምንም መልኩ ልክ አይደለም፤ በሰው ሀገር ስንከፋ የሚሰማን ስሜት ፣ ከራሳችን ሀገር ከሚደርስብን የጥቃት ስሜት ጋር ካነጻጸርነው ግን፣ የሕመሙ ክብደት በሰው ሀገር
ሲሆን ይቀንሳል።
ሀገር ያስከፋን ጊዜ ግን ወዴት አቤት ይባላል? የራስ ሕዝብስ ለማን ይከሰሳል?" እያለች ምሯን ትናገራለች።
እናቴ አሳዛኝና አንጀት ቆራጭ ነገሮች ሲገጥሟት፦ "ከቀላድም ባይረዝም ከመጫኛም ባይበልጥ፤
አንጀት ያልቅ የለም ወይ ሲቆረጥ ሲቆረጥ።" ትላለች ።
የማኅበረሰባዊ መገፋት አንጀት ይቆርጣል ፤ አይመልሰኝ አሰኝቶ ድንጋይ ያስወረውራል። በጊዜ ሊታረም ከዘመኑ ጋርም ሊዘምን የሚገባ እንጅ የምናጌጥበት ነውር መሆን የለበትም ።
👉በፈረንጅ ሚስት መጽሐፍ
ደራሲዋ እስከዳር ግርማይና መሰል የፈረንጅ ሚስቶች ያለፈና ያለን ቁስል በቃላት አስጊጣ በመግለጧ ግላዊ እፎይታ ፣ ሕሊናዊ ፈውስ አግኝተውበታል፤ ብዬ ተስፋ አደርጋለሁ ።
በመሰል ፈተና ውስጥ ያሉ ሰዎች የግለ ማስታወሻዎቹን ሂደትና መፍትሔ አይተው ተስፋ የሚሰጥ ትምህርት ያገኛሉ። በማኅበረሰባዊ ሂሷም ብዙዎች ራሳቸውን እንዲታዘቡ ራሳቸውን እንዲመረምሩና እንዲታረሙ ኮርኩራለች።
እስከዳር በራሷ የተወሰነ ዘመንና ማኅበረሰብ ውስጥ ለፈረንጅ ሚስት የነበረን አመለካከት ለትውልድ በማስተላለፍ የታሪክ ምስክር በመሆን፤ ለፈረንጅ ሚስቶች ሐውልት አቁማለች።
ማጠቃለያ
ደራሲ እስከዳር ግርማይ በመጽሐፏ ውስጥ 'የፈረንጅ ሚስት' የሚለውን ስም ከስድብነት ወደ ማንነት (Identity)፣ ከማንነትም ወደ ተጋድሎ (Resistance) ቀይራዋለች። ይህ መጽሐፍ የአንድን ግለሰብ ሕይወት ብቻ ሳይሆን፣ የኢትዮጵያዊነትን እና የዘመናዊነትን (Modernity) ግጭት፣ እንዲሁም የሴትነትን ነፃነት የሚፈትን፣ ማኅበረሰባዊ ሕጸፅን ነቅሶ የሚያሳይ መስታወት ነው።
👉እስከዬ አሁንም ያላወጣሽው ብዙ ግላዊ "የመሬማውያን ጉዳይ" አለና በጥልቀት ቆፍረሽ ታወጭው ዘንድ አደራ እላለሁ 🙏
👉የፈረንጅ ሚስት በዶክመንተሪ ቢዘጋጅ ደግሞ ከንባብ የራቀውና የስድብ መጋዘን ከሆነው የማኅበረሰብ ክፍል ውስጥ በእጁ ላይ ገብተሽ ትነግሪዋለሽ። የፈረንጅ ሚስት ማለት በምን የሕይወት ሸለቆ ውስጥ አልፋ ምርጫዋን የምታስከብር እንደሆነች ታሳያቸዋለሽ።
የሀብከ ብርሃኔ ጥላሁን
Sponsored by
Surafel
1 month ago
ሜታ በቢሊዮን የሚቆጠር ዶላር ለሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) በማውጣቱ ሳቢያ 8,000 ሠራተኞችን ሊቀንስ ነው
#fastmereja I የፌስቡክ እና የኢንስታግራም እናት ኩባንያ የሆነው ሜታ፣ ለሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) ፕሮጀክቶች የሚያወጣውን ወጪ በከፍተኛ ሁኔታ ለመጨመር በማቀዱ የጠቅላላ ሰራተኞቹን 10 በመቶ ወይም 8,000 ያህል ሰራተኞችን በሚቀጥለው ወር ከስራ እንደሚያሰናብት አስታወቀ። ኩባንያው ከዚህ በተጨማሪ ቀደም ሲል ክፍት የነበሩ በሺዎች የሚቆጠሩ የሥራ መደቦችን እንደማይሞላ ለሠራተኞቹ ባስተላለፈው የውስጥ ማስታወሻ ገልጿል።
የሜታ ዋና ስራ አስፈጻሚ ማርክ ዙከርበርግ በዘንድሮው ዓመት ብቻ ለሰው ሰራሽ አስተውሎት ልማት 135 ቢሊዮን ዶላር ወጪ ለማድረግ ማቀዳቸውን ተከትሎ ይህ የሠራተኛ ቅነሳ መወሰኑ ተገልጿል። ይህ የወጪ መጠን ኩባንያው ባለፉት ሶስት ዓመታት በድምሩ ለዘርፉ ካወጣው ገንዘብ ጋር እኩል ነው። ዙከርበርግ የ"AI" መሣሪያዎችን የሚጠቀሙ ሠራተኞች ምርታማነት መጨመሩን በመጥቀስ፣ ቀደም ሲል ትልቅ ቡድን የሚጠይቁ ሥራዎችን አሁን በአንድ ሰው ማከናወን እንደሚቻል በጥር ወር ላይ መናገራቸው ይታወሳል።
ከሥራ ቅነሳው ጎን ለጎን ሜታ የ"AI" ሞዴሎችን ለማሰልጠን የሠራተኞቹን የኮምፒውተር እንቅስቃሴ መከታተል መጀመሩ በሠራተኞች ዘንድ ቅሬታን ፈጥሯል። ኩባንያው እ.ኤ.አ. ከ2022 ጀምሮ በተለያዩ ዙሮች በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ ሠራተኞችን የቀነሰ ቢሆንም፣ የዘንድሮው እርምጃ ከ2023 ወዲህ የተመዘገበ ትልቁ የሥራ ስንብት ይሆናል።
ይህ በቴክኖሎጂው ዘርፍ የታየው የሠራተኛ ቅነሳ ማዕበል ሜታን ብቻ ሳይሆን ሌሎች ታላላቅ ኩባንያዎችንም አጠቃሏል። አማዞን 30,000፣ ኦራክል 10,000 እንዲሁም ማይክሮሶፍት በሺዎች ለሚቆጠሩ ነባር ሠራተኞቹ በፈቃደኝነት የሥራ ስንብት ክፍያ እያቀረበ ይገኛል። አብዛኞቹ ኩባንያዎች ለውሳኔያቸው እንደ ምክንያት የጠቀሱት የሰው ሰራሽ አስተውሎት አቅም እያደገ መምጣቱንና ለዘርፉ የሚመደበው መዋዕለ ንዋይ መጨመሩን ነው።
#fastmereja I የፌስቡክ እና የኢንስታግራም እናት ኩባንያ የሆነው ሜታ፣ ለሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) ፕሮጀክቶች የሚያወጣውን ወጪ በከፍተኛ ሁኔታ ለመጨመር በማቀዱ የጠቅላላ ሰራተኞቹን 10 በመቶ ወይም 8,000 ያህል ሰራተኞችን በሚቀጥለው ወር ከስራ እንደሚያሰናብት አስታወቀ። ኩባንያው ከዚህ በተጨማሪ ቀደም ሲል ክፍት የነበሩ በሺዎች የሚቆጠሩ የሥራ መደቦችን እንደማይሞላ ለሠራተኞቹ ባስተላለፈው የውስጥ ማስታወሻ ገልጿል።
የሜታ ዋና ስራ አስፈጻሚ ማርክ ዙከርበርግ በዘንድሮው ዓመት ብቻ ለሰው ሰራሽ አስተውሎት ልማት 135 ቢሊዮን ዶላር ወጪ ለማድረግ ማቀዳቸውን ተከትሎ ይህ የሠራተኛ ቅነሳ መወሰኑ ተገልጿል። ይህ የወጪ መጠን ኩባንያው ባለፉት ሶስት ዓመታት በድምሩ ለዘርፉ ካወጣው ገንዘብ ጋር እኩል ነው። ዙከርበርግ የ"AI" መሣሪያዎችን የሚጠቀሙ ሠራተኞች ምርታማነት መጨመሩን በመጥቀስ፣ ቀደም ሲል ትልቅ ቡድን የሚጠይቁ ሥራዎችን አሁን በአንድ ሰው ማከናወን እንደሚቻል በጥር ወር ላይ መናገራቸው ይታወሳል።
ከሥራ ቅነሳው ጎን ለጎን ሜታ የ"AI" ሞዴሎችን ለማሰልጠን የሠራተኞቹን የኮምፒውተር እንቅስቃሴ መከታተል መጀመሩ በሠራተኞች ዘንድ ቅሬታን ፈጥሯል። ኩባንያው እ.ኤ.አ. ከ2022 ጀምሮ በተለያዩ ዙሮች በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ ሠራተኞችን የቀነሰ ቢሆንም፣ የዘንድሮው እርምጃ ከ2023 ወዲህ የተመዘገበ ትልቁ የሥራ ስንብት ይሆናል።
ይህ በቴክኖሎጂው ዘርፍ የታየው የሠራተኛ ቅነሳ ማዕበል ሜታን ብቻ ሳይሆን ሌሎች ታላላቅ ኩባንያዎችንም አጠቃሏል። አማዞን 30,000፣ ኦራክል 10,000 እንዲሁም ማይክሮሶፍት በሺዎች ለሚቆጠሩ ነባር ሠራተኞቹ በፈቃደኝነት የሥራ ስንብት ክፍያ እያቀረበ ይገኛል። አብዛኞቹ ኩባንያዎች ለውሳኔያቸው እንደ ምክንያት የጠቀሱት የሰው ሰራሽ አስተውሎት አቅም እያደገ መምጣቱንና ለዘርፉ የሚመደበው መዋዕለ ንዋይ መጨመሩን ነው።
1 month ago
ጠ/ሚ'ሯ የተሾሙሏት ኢትዮጵያ AI በጤና ዘርፍ ላይ ምን ያህል ድርሻ አለው?
#ethiopia | ኢትዮጵያ በሕክምናው ዘርፍ ለበርካታ ዓመታት ሲፈታተኗት የነበሩትን የባለሙያ እጥረት፣ የምርመራ መዘግየት እና የመረጃ አያያዝ ክፍተቶችን ለመቅረፍ ሰው ሰራሽ አስተውሎትን (AI) እንደ ዋነኛ መፍትሔ መጠቀም ጀምራለች።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተለያዩ ጊዜያት እንደገለጹት፤ ሰው ሠራሽ አስተውሎት ለኢትዮጵያ የቅንጦት ጉዳይ ሳይሆን ፍትሃዊ የጤና አገልግሎት ለማቅረብ የግድ አስፈላጊ መሠረታዊ ግብዓት ነው።
ቀደም ባሉት ጊዜያት የራጅ ወይም የሲቲ ስካን ውጤቶችን ለመተርጎም ቀናትን አልፎ ተርፎም ሳምንታትን ይፈጅ የነበረ ሲሆን፣ ይህ መዘግየት ሀገራችን ወደ ሰው ሠራሽ አስተውሎት ቴክኖሎጂ አማራጭ እንድትመለከት አስገድዷታል።
በአሁኑ ወቅት ሀገራችን በራሷ ባለሙያዎች የበለጸጉ እና ከነባራዊ ሁኔታዎቿ ጋር የተቃኙ የAI መተግበሪያዎች ባለቤት መሆን ችላለች።
የኢትዮጵያ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ያበለጸገው "መላ" የተሰኘው መተግበሪያ በዘርፉ የታየ ትልቅ እመርታ ነው።
መተግበሪያው ፈጣን የምርመራ ውጤቶችን በመስጠት የሳንባ ነቀርሳን (TB) እና የሳንባ ምችን (Pneumonia) ከራጅ ምስሎች ላይ በሰከንዶች ውስጥ በመለየት ለሐኪሞች የውሳኔ ድጋፍ ይሰጣል።
ከዚህ በተጨማሪ የጡት ካንሰር ምርመራ የራጅ (Mammography) ምስሎችን በመተንተን የሕመሙን ምልክቶች በከፍተኛ ፍጥነትና ጥራት የመለየት ተግባር ያከናውናል።
ካንሰርን ገና በጅምሩ ለመለየት ያለው አቅም የብዙዎችን ሕይወት ለማዳን ወሳኝ ሚና የሚጫወት ሲሆን፤ በአሁኑ ወቅት በጥቁር አንበሳ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል እና በቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሊኒየም ሕክምና ኮሌጅ አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል።
በሌላ በኩል የደረት ራጅ ምስሎችን በማንበብ የሳንባ ነቀርሳና ቲቢን የሚለየው ቴክኖሎጂ (CXR-based Diagnosis) የራጅ ባለሙያዎች በሌሉባቸው አካባቢዎች ፈጣን ውሳኔ ለመስጠት እያስቻለ ነው።
ይህ አገልግሎት በየካ ኮቲቤ አጠቃላይ ሆስፒታል እና በተመረጡ የክልል ሆስፒታሎች ተግባራዊ ተደርጓል።
የማህፀን በር ካንሰር ምርመራ (Cervical Cancer Screening) በምስል ትንተና አማካኝነት ምልክቶችን ቀድሞ መለየት የሚያስችል ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት በጋንዲ መታሰቢያ ሆስፒታልና በአንዳንድ የጤና ጣቢያዎች በሙከራ ሂደት ላይ ይገኛል።
በተመሳሳይ የልብ ምትን (ECG) በመተንተን የሕመም ዓይነቶችን የሚለየው የሰው ሠራሽ አስተውሎት (AI) መተግበሪያ የልብ ስፔሻሊስቶች በሌሉባቸው ሆስፒታሎች ለጠቅላላ ሐኪሞች እንደ ረዳት መሣሪያ ሆኖ እያገለገለ ነው።
እነዚህ የቴክኖሎጂ ውጤቶች በዋናነት በመንግሥት ከፍተኛ የሪፈራል ሆስፒታሎች የተጀመሩ ቢሆንም፣ ቀስ በቀስ ወደ ሁሉም የሀገራችን አካባቢዎች የማስፋፋት ሥራ እየተከናወነ ይገኛል።
የኢትዮጵያ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት እና የጤና ሚኒስቴር በቅንጅት እያከናወኑት ያለው ይህ ተግባር የምርመራ ጥራትን በማሻሻል የሀገራችንን የጤና አገልግሎት ወደ አዲስ ከፍታ እያሸጋገረው ይገኛል።
ማስታወሻ ፦ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአፍሪካ ሕብረት የሰው ሰራሽ አስተውሎት (Artificial Intelligence) እና የዲጂታል ጤና ዘርፍ መሪ (Champion) ሆነው ተሹመዋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን) #getutemesgen #getu via#ebc #ethiopia #aiinhealth #healthtech #digitalhealth #melaai #ethiopianaiinstitute
#ethiopia | ኢትዮጵያ በሕክምናው ዘርፍ ለበርካታ ዓመታት ሲፈታተኗት የነበሩትን የባለሙያ እጥረት፣ የምርመራ መዘግየት እና የመረጃ አያያዝ ክፍተቶችን ለመቅረፍ ሰው ሰራሽ አስተውሎትን (AI) እንደ ዋነኛ መፍትሔ መጠቀም ጀምራለች።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተለያዩ ጊዜያት እንደገለጹት፤ ሰው ሠራሽ አስተውሎት ለኢትዮጵያ የቅንጦት ጉዳይ ሳይሆን ፍትሃዊ የጤና አገልግሎት ለማቅረብ የግድ አስፈላጊ መሠረታዊ ግብዓት ነው።
ቀደም ባሉት ጊዜያት የራጅ ወይም የሲቲ ስካን ውጤቶችን ለመተርጎም ቀናትን አልፎ ተርፎም ሳምንታትን ይፈጅ የነበረ ሲሆን፣ ይህ መዘግየት ሀገራችን ወደ ሰው ሠራሽ አስተውሎት ቴክኖሎጂ አማራጭ እንድትመለከት አስገድዷታል።
በአሁኑ ወቅት ሀገራችን በራሷ ባለሙያዎች የበለጸጉ እና ከነባራዊ ሁኔታዎቿ ጋር የተቃኙ የAI መተግበሪያዎች ባለቤት መሆን ችላለች።
የኢትዮጵያ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ያበለጸገው "መላ" የተሰኘው መተግበሪያ በዘርፉ የታየ ትልቅ እመርታ ነው።
መተግበሪያው ፈጣን የምርመራ ውጤቶችን በመስጠት የሳንባ ነቀርሳን (TB) እና የሳንባ ምችን (Pneumonia) ከራጅ ምስሎች ላይ በሰከንዶች ውስጥ በመለየት ለሐኪሞች የውሳኔ ድጋፍ ይሰጣል።
ከዚህ በተጨማሪ የጡት ካንሰር ምርመራ የራጅ (Mammography) ምስሎችን በመተንተን የሕመሙን ምልክቶች በከፍተኛ ፍጥነትና ጥራት የመለየት ተግባር ያከናውናል።
ካንሰርን ገና በጅምሩ ለመለየት ያለው አቅም የብዙዎችን ሕይወት ለማዳን ወሳኝ ሚና የሚጫወት ሲሆን፤ በአሁኑ ወቅት በጥቁር አንበሳ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል እና በቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሊኒየም ሕክምና ኮሌጅ አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል።
በሌላ በኩል የደረት ራጅ ምስሎችን በማንበብ የሳንባ ነቀርሳና ቲቢን የሚለየው ቴክኖሎጂ (CXR-based Diagnosis) የራጅ ባለሙያዎች በሌሉባቸው አካባቢዎች ፈጣን ውሳኔ ለመስጠት እያስቻለ ነው።
ይህ አገልግሎት በየካ ኮቲቤ አጠቃላይ ሆስፒታል እና በተመረጡ የክልል ሆስፒታሎች ተግባራዊ ተደርጓል።
የማህፀን በር ካንሰር ምርመራ (Cervical Cancer Screening) በምስል ትንተና አማካኝነት ምልክቶችን ቀድሞ መለየት የሚያስችል ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት በጋንዲ መታሰቢያ ሆስፒታልና በአንዳንድ የጤና ጣቢያዎች በሙከራ ሂደት ላይ ይገኛል።
በተመሳሳይ የልብ ምትን (ECG) በመተንተን የሕመም ዓይነቶችን የሚለየው የሰው ሠራሽ አስተውሎት (AI) መተግበሪያ የልብ ስፔሻሊስቶች በሌሉባቸው ሆስፒታሎች ለጠቅላላ ሐኪሞች እንደ ረዳት መሣሪያ ሆኖ እያገለገለ ነው።
እነዚህ የቴክኖሎጂ ውጤቶች በዋናነት በመንግሥት ከፍተኛ የሪፈራል ሆስፒታሎች የተጀመሩ ቢሆንም፣ ቀስ በቀስ ወደ ሁሉም የሀገራችን አካባቢዎች የማስፋፋት ሥራ እየተከናወነ ይገኛል።
የኢትዮጵያ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት እና የጤና ሚኒስቴር በቅንጅት እያከናወኑት ያለው ይህ ተግባር የምርመራ ጥራትን በማሻሻል የሀገራችንን የጤና አገልግሎት ወደ አዲስ ከፍታ እያሸጋገረው ይገኛል።
ማስታወሻ ፦ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአፍሪካ ሕብረት የሰው ሰራሽ አስተውሎት (Artificial Intelligence) እና የዲጂታል ጤና ዘርፍ መሪ (Champion) ሆነው ተሹመዋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን) #getutemesgen #getu via#ebc #ethiopia #aiinhealth #healthtech #digitalhealth #melaai #ethiopianaiinstitute
2 months ago
"ከሰላምታ ጋር" ምሽት
እንኳን አደረሳችሁ።
አንጋፋ የኪነጥበብ ምሽት!
እባክዎ ሸር በማድረግ ተባበሩን!
51ኛው የባህል ማዕከል የኪነጥበብ ምሽት ረቡዕ ሚያዚያ 7፥2018 ዓ.ም ይካሄዳል።በዕለቱም ተወዳጇና ዝነኛዋ ፀሀፊ ተውኔትና አዘጋጅ መዓዛ ወርቁ የክብር እንግዳችን ሆና በመካከላችን በመገኘት ሙያዊ ልምዷን ታካፍለናለች።
መድረኩን ዳንኤል ወርቅነህ ያጋፍረዋል።
እንዲሁም ግጥሞች ፣ ወግ ፣ ሙዚቃና ሞኖሎግ ለእናንተ ውድ ታዳሚዎቻችንን በባህል ማዕከል አዳራሽ ከቀኑ በ 11: 30 ጀምሮ ተሰናድቶ ይጠብቃችኃል።
#ማስታወሻ :— ፕሮግራሙ ላይ ለመታደም የምትፈልጉ በአሁን ሰዓት የዩኒቨርስቲው ተማሪ ያልሆናችሁ የስነ-ጽሑፍ አፍቃሪያን መግቢያው በ5ተኛ በር በኩል ነው።
እንኳን አደረሳችሁ።
አንጋፋ የኪነጥበብ ምሽት!
እባክዎ ሸር በማድረግ ተባበሩን!
51ኛው የባህል ማዕከል የኪነጥበብ ምሽት ረቡዕ ሚያዚያ 7፥2018 ዓ.ም ይካሄዳል።በዕለቱም ተወዳጇና ዝነኛዋ ፀሀፊ ተውኔትና አዘጋጅ መዓዛ ወርቁ የክብር እንግዳችን ሆና በመካከላችን በመገኘት ሙያዊ ልምዷን ታካፍለናለች።
መድረኩን ዳንኤል ወርቅነህ ያጋፍረዋል።
እንዲሁም ግጥሞች ፣ ወግ ፣ ሙዚቃና ሞኖሎግ ለእናንተ ውድ ታዳሚዎቻችንን በባህል ማዕከል አዳራሽ ከቀኑ በ 11: 30 ጀምሮ ተሰናድቶ ይጠብቃችኃል።
#ማስታወሻ :— ፕሮግራሙ ላይ ለመታደም የምትፈልጉ በአሁን ሰዓት የዩኒቨርስቲው ተማሪ ያልሆናችሁ የስነ-ጽሑፍ አፍቃሪያን መግቢያው በ5ተኛ በር በኩል ነው።
2 months ago
ከገንዘብ በላይ የታማኝነት ልክ
#fastmereja I በብሔራዊ ሙዚየም የትኬት ሽያጭ ባለሙያ የሆኑት ወ/ሮ ጌራወርቅ አሰፋ፣ አንድ ቻይናዊ ጎብኝ የዘነጋውን 47 ሺህ ብር የያዘ ቦርሳ በታማኝነት በመመለስ የሀገርን ገጽታ የሚያስከብር ተግባር ፈጽመዋል።
የካቲት 7 ቀን 2018 ዓ.ም ሶንግ ጆንግ የተባለ ቻይናዊ ጎብኝ ከጓደኞቹ ጋር በብሔራዊ ሙዚየም ያደረገውን ጉብኝት አጠናቆ ሲወጣ፣ 47 ሺህ የኢትዮጵያ ብር የያዘ ቦርሳውን ዘንግቶት ነበር። ቦርሳው የወደቀው በትኬት መቁረጫ መስኮት አካባቢ ሲሆን፣ ወ/ሮ ጌራወርቅ አሰፋ ቦርሳውን እንዳገኘች ለባልደረቦቿ በማሳወቅ በጥንቃቄ ጠብቃ እንዲቆይ አድርጋለች።
ከአራት ሰዓታት በኋላ ቻይናዊው ጎብኝ በከፍተኛ ጭንቀት ወደ ሙዚየሙ ቢመለስም፣ የጠፋበትን ገንዘብ አንድም ሳንቲም ሳይጎድል ተረክቧል። ወ/ሮ ጌራወርቅ ለኤኤምኤን (AMN) በሰጠችው ቃል፣ "ገንዘቡን ስመልስ ከእሱ በላይ ትልቅ ሸክም እንደወረደልኝ ተሰምቶኝ እፎይታ አግኝቻለሁ" ስትል ገልጻለች።
ጎብኚው ሶንግ ጆንግ በኢትዮጵያውያን ቅንነት እጅግ መገረሙን በመግለጽ፣ የወ/ሮ ጌራወርቅን ታማኝነት የሚገልጽ የምስጋና ማስታወሻ በገዛ እጁ አስፍሯል።
የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን የብሔራዊ ሙዚየም መሪ ስራ አስፈፃሚ፣ ለባለሙያዋ የምስጋና ደብዳቤና እውቅና መስጠታቸውን አስታውቀዋል። ይህ ተግባር በቱሪዝም ዘርፉ ላይ ለሚሰሩ ባለሙያዎች ትልቅ የሥነ-ምግባር አርአያ ተደርጎ ተወስዷል።
#fastmereja I በብሔራዊ ሙዚየም የትኬት ሽያጭ ባለሙያ የሆኑት ወ/ሮ ጌራወርቅ አሰፋ፣ አንድ ቻይናዊ ጎብኝ የዘነጋውን 47 ሺህ ብር የያዘ ቦርሳ በታማኝነት በመመለስ የሀገርን ገጽታ የሚያስከብር ተግባር ፈጽመዋል።
የካቲት 7 ቀን 2018 ዓ.ም ሶንግ ጆንግ የተባለ ቻይናዊ ጎብኝ ከጓደኞቹ ጋር በብሔራዊ ሙዚየም ያደረገውን ጉብኝት አጠናቆ ሲወጣ፣ 47 ሺህ የኢትዮጵያ ብር የያዘ ቦርሳውን ዘንግቶት ነበር። ቦርሳው የወደቀው በትኬት መቁረጫ መስኮት አካባቢ ሲሆን፣ ወ/ሮ ጌራወርቅ አሰፋ ቦርሳውን እንዳገኘች ለባልደረቦቿ በማሳወቅ በጥንቃቄ ጠብቃ እንዲቆይ አድርጋለች።
ከአራት ሰዓታት በኋላ ቻይናዊው ጎብኝ በከፍተኛ ጭንቀት ወደ ሙዚየሙ ቢመለስም፣ የጠፋበትን ገንዘብ አንድም ሳንቲም ሳይጎድል ተረክቧል። ወ/ሮ ጌራወርቅ ለኤኤምኤን (AMN) በሰጠችው ቃል፣ "ገንዘቡን ስመልስ ከእሱ በላይ ትልቅ ሸክም እንደወረደልኝ ተሰምቶኝ እፎይታ አግኝቻለሁ" ስትል ገልጻለች።
ጎብኚው ሶንግ ጆንግ በኢትዮጵያውያን ቅንነት እጅግ መገረሙን በመግለጽ፣ የወ/ሮ ጌራወርቅን ታማኝነት የሚገልጽ የምስጋና ማስታወሻ በገዛ እጁ አስፍሯል።
የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን የብሔራዊ ሙዚየም መሪ ስራ አስፈፃሚ፣ ለባለሙያዋ የምስጋና ደብዳቤና እውቅና መስጠታቸውን አስታውቀዋል። ይህ ተግባር በቱሪዝም ዘርፉ ላይ ለሚሰሩ ባለሙያዎች ትልቅ የሥነ-ምግባር አርአያ ተደርጎ ተወስዷል።
2 months ago
የኮንጎ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት የዕድሜ ልክ እስራት ተፈረደባቸው
#ethiopia | የኮንጎ ሪፐብሊክ (ኮንጎ ብራዛቪል) ከፍተኛ ፍርድ ቤት የሀገሪቱ እግር ኳስ ፌዴሬሽን (FECOFOOT) ፕሬዝዳንት ዦን ጋይ ብሌዝ ማዮላስ (Jean-Guy Blaise Mayolas) በከባድ የሙስና ወንጀል ጥፋተኛ ሆነው በመገኘታቸው የዕድሜ ልክ እስራት ፈረደባቸው።
ፕሬዝዳንቱ የተፈረደባቸው በሚከተሉት የወንጀል ድርጊቶች ተሳትፈው በመገኘታቸው ነው፦
የገንዘብ ምዝበራ፦
ከዓለም አቀፉ እግር ኳስ ማኅበር (FIFA) ለኮንጎ እግር ኳስ እድገት የተላከ ከ1.1 ሚሊዮን ዶላር በላይ ለግል ጥቅም ማዋል፤
የኮቪድ-19 ፈንድ ስርቆት፦
ፊፋ በወረርሽኙ ወቅት ለሴቶች እግር ኳስ ልማት የመደበውን 500,000 ዶላር ለታለመለት ዓላማ አለማዋል፤
የሰነድ ማጭበርበር እና የጥቅም ግጭት፦ የፌዴሬሽኑን ገንዘብ ለማጭበርበር የሀሰት ሰነዶችን መጠቀም እና ከቤተሰብ አባላት ጋር የተገናኙ የጥቅም ግጭቶች።
ባለፈው ሳምንት (መጋቢት 2026) በብራዛቪል የወንጀል ችሎት የተሰጠው ውሳኔ የሚከተሉትን አካቷል፦
ዦን ጋይ ብሌዝ ማዮላስ፦
በሌሉበት (In absentia) የዕድሜ ልክ እስራት፤
ሊዮኔል ማዮላስ (የፕሬዝዳንቱ ልጅ)፦
በተመሳሳይ ክስ የዕድሜ ልክ እስራት፤
ባጂ ሞምቦ ዋንቴቴ (የፌዴሬሽኑ ዋና ጸሐፊ)፦ የ5 ዓመት እስራት፤
ራውል ካንዳ (የፌዴሬሽኑ ገንዘብ ያዥ)፦ የ5 ዓመት እስራት።
ማስታወሻ፦
ፕሬዝዳንቱ ማዮላስ ፍርዱ በሚሰጥበት ወቅት በችሎት ያልተገኙ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት የት እንዳሉ እንደማይታወቅና በፖሊስ እየታደኑ መሆኑ ተነግሯል።
ይህ ክስተት ፊፋ ቀደም ሲል በፌዴሬሽኑ ላይ ጥሎት የነበረውን እገዳ እና በኮንጎ እግር ኳስ ላይ የነበረውን የአስተዳደር ቀውስ ተከትሎ የመጣ ነው።
#ethiopia | የኮንጎ ሪፐብሊክ (ኮንጎ ብራዛቪል) ከፍተኛ ፍርድ ቤት የሀገሪቱ እግር ኳስ ፌዴሬሽን (FECOFOOT) ፕሬዝዳንት ዦን ጋይ ብሌዝ ማዮላስ (Jean-Guy Blaise Mayolas) በከባድ የሙስና ወንጀል ጥፋተኛ ሆነው በመገኘታቸው የዕድሜ ልክ እስራት ፈረደባቸው።
ፕሬዝዳንቱ የተፈረደባቸው በሚከተሉት የወንጀል ድርጊቶች ተሳትፈው በመገኘታቸው ነው፦
የገንዘብ ምዝበራ፦
ከዓለም አቀፉ እግር ኳስ ማኅበር (FIFA) ለኮንጎ እግር ኳስ እድገት የተላከ ከ1.1 ሚሊዮን ዶላር በላይ ለግል ጥቅም ማዋል፤
የኮቪድ-19 ፈንድ ስርቆት፦
ፊፋ በወረርሽኙ ወቅት ለሴቶች እግር ኳስ ልማት የመደበውን 500,000 ዶላር ለታለመለት ዓላማ አለማዋል፤
የሰነድ ማጭበርበር እና የጥቅም ግጭት፦ የፌዴሬሽኑን ገንዘብ ለማጭበርበር የሀሰት ሰነዶችን መጠቀም እና ከቤተሰብ አባላት ጋር የተገናኙ የጥቅም ግጭቶች።
ባለፈው ሳምንት (መጋቢት 2026) በብራዛቪል የወንጀል ችሎት የተሰጠው ውሳኔ የሚከተሉትን አካቷል፦
ዦን ጋይ ብሌዝ ማዮላስ፦
በሌሉበት (In absentia) የዕድሜ ልክ እስራት፤
ሊዮኔል ማዮላስ (የፕሬዝዳንቱ ልጅ)፦
በተመሳሳይ ክስ የዕድሜ ልክ እስራት፤
ባጂ ሞምቦ ዋንቴቴ (የፌዴሬሽኑ ዋና ጸሐፊ)፦ የ5 ዓመት እስራት፤
ራውል ካንዳ (የፌዴሬሽኑ ገንዘብ ያዥ)፦ የ5 ዓመት እስራት።
ማስታወሻ፦
ፕሬዝዳንቱ ማዮላስ ፍርዱ በሚሰጥበት ወቅት በችሎት ያልተገኙ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት የት እንዳሉ እንደማይታወቅና በፖሊስ እየታደኑ መሆኑ ተነግሯል።
ይህ ክስተት ፊፋ ቀደም ሲል በፌዴሬሽኑ ላይ ጥሎት የነበረውን እገዳ እና በኮንጎ እግር ኳስ ላይ የነበረውን የአስተዳደር ቀውስ ተከትሎ የመጣ ነው።
Sponsored by
Surafel
2 months ago
ጉዳዩ- የፍራፍሬ ቀንን ስለማክበር
ውድ ወላጆች ሰኞ ማለትም 21/07/2018 ዓ.ም ልጆች ጤናማ የአመጋገብ ልምድን እንዲያዳብሩ፣ ስለ ተለያዩ የፍራፍሬ አይነቶች እና ጥቅሞቻቸው ግንዛቤ እንዲያገኙ ለማድረግ በትምህርት ቤታችን "የፍራፍሬ ቀን" ለማክበር ታቅዷል።
ይህ ዝግጅት ተማሪዎች በጋራ በመሆን የተፈጥሮ ስጦታ የሆኑትን ፍራፍሬዎች የሚቀምሱበትና የሚማሩበት ልዩ ቀን ይሆናል። ስለሆነም ለልጅዎ ከታች የተገለጸውን የፍራፍሬ አይነት እንዲለኩልን በትህትና እንጠይቃለን።
ማሳሰቢያ :- ማንጎ ግማሽ ኪሎ እንዲልኩልን።
ይህ በአዲስ አበበባ ውስጥ የሚገኝ አንድ ትምህርት ቤት ለወላጆች የላከው ማስታወሻ ነው።
ለመማር ማስተማሩ እንዲህ ያለው ነገር ጠቀሜታው ምንድን ነው?
ልጆቾን በሚያስተምሩበት ት/ት ቤት እንዲህ ያለ ልማድ አለ?
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
ውድ ወላጆች ሰኞ ማለትም 21/07/2018 ዓ.ም ልጆች ጤናማ የአመጋገብ ልምድን እንዲያዳብሩ፣ ስለ ተለያዩ የፍራፍሬ አይነቶች እና ጥቅሞቻቸው ግንዛቤ እንዲያገኙ ለማድረግ በትምህርት ቤታችን "የፍራፍሬ ቀን" ለማክበር ታቅዷል።
ይህ ዝግጅት ተማሪዎች በጋራ በመሆን የተፈጥሮ ስጦታ የሆኑትን ፍራፍሬዎች የሚቀምሱበትና የሚማሩበት ልዩ ቀን ይሆናል። ስለሆነም ለልጅዎ ከታች የተገለጸውን የፍራፍሬ አይነት እንዲለኩልን በትህትና እንጠይቃለን።
ማሳሰቢያ :- ማንጎ ግማሽ ኪሎ እንዲልኩልን።
ይህ በአዲስ አበበባ ውስጥ የሚገኝ አንድ ትምህርት ቤት ለወላጆች የላከው ማስታወሻ ነው።
ለመማር ማስተማሩ እንዲህ ያለው ነገር ጠቀሜታው ምንድን ነው?
ልጆቾን በሚያስተምሩበት ት/ት ቤት እንዲህ ያለ ልማድ አለ?
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
2 months ago
170,000,000 ብር የእንጦጦ ኪዳነምሕረት የገቢ ማሰባሰቢያ
ሪከርድ በመስበር ተጠናቀቀ
ከመጋቢት 11 እሰ መጋቢት 12/2018 በእንጦጦ ኪዳነምሕረት አዳራሽ ሲከናወን የነበረው የገቢ ማሰባሰቢያ መርሐግብር 170,000,000.000 /አንድ መቶ ሰባ ሚሊያን/ ብር በመሰብሰብ ተጠናቀቀ።
ከዚኽ ውስጥ 139,000,000.00 ሚሊዬን ብር የተረጋገጠ ሲሆን ቀሪው 31 ሚሊዬ ብር ደግሞ ቃል የተገባ ሲሆን በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ ተጠናቆ ይገባል ተብሎ ይጠበቃል።
ይኽንን መሥሐግብር ብፁዕ አቡነ መቃርዮስ የምዕራብ ካናዳ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ መልአከ አሚን ቆሞስ አባ ገብረ ሥላሴ ይርሳው የገዳሟ ዋና አበመኔት፣ ማኅበረ መነኮሳቱ፣ ማኅበረ መነኮሳቱ፣ መምህራን፣ ዘማርያን፣ ምእመናን በሀገር ውስጥ እና በውጭ ሦስቱንም ሌሊት በንቃት ተሳትፈውበታል።
ቲክታከሮች፣ ዩቱበሮች እና የኪነጥበብ ባለሙያዎች ዶክመንተሪ፣ ማስታወቂያ፣ ቀጥታ ሥርጭት መርሐግብሩን በትሩፋት በማገልገላቸው ከገዳሟ አበው መነኮሳት ማስታወሻ እንዲኾናቸው መንበሯ ላይ ያለችውን የድንግል ማርያም ሥዕለ አድኅኖ እና ሠርተፍኬት በስጦታ ተበርክቶላቸዋል።
ይኽንን ኹነት ከኮሚቴው ጋር በመተባበር የማስተባበር እና የማማከር ተግባር ለአንድ ወር ያከናወነው ሎዛ ኹነቶች - Liza Events በትሩፋት በማገልገሉ መንበሯ ላይ ያለችውን የድንግል ማርያም ሥዕለ አድኅኖ፣ የወርቅ ካባ እና ሠርተፍኬት ከብፁዕ አቡነ መቃርዮስ እና ከገዳሙ አበመኔት እጅ በስጦታ ተበርክቶለታል።
ሪከርድ በመስበር ተጠናቀቀ
ከመጋቢት 11 እሰ መጋቢት 12/2018 በእንጦጦ ኪዳነምሕረት አዳራሽ ሲከናወን የነበረው የገቢ ማሰባሰቢያ መርሐግብር 170,000,000.000 /አንድ መቶ ሰባ ሚሊያን/ ብር በመሰብሰብ ተጠናቀቀ።
ከዚኽ ውስጥ 139,000,000.00 ሚሊዬን ብር የተረጋገጠ ሲሆን ቀሪው 31 ሚሊዬ ብር ደግሞ ቃል የተገባ ሲሆን በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ ተጠናቆ ይገባል ተብሎ ይጠበቃል።
ይኽንን መሥሐግብር ብፁዕ አቡነ መቃርዮስ የምዕራብ ካናዳ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ መልአከ አሚን ቆሞስ አባ ገብረ ሥላሴ ይርሳው የገዳሟ ዋና አበመኔት፣ ማኅበረ መነኮሳቱ፣ ማኅበረ መነኮሳቱ፣ መምህራን፣ ዘማርያን፣ ምእመናን በሀገር ውስጥ እና በውጭ ሦስቱንም ሌሊት በንቃት ተሳትፈውበታል።
ቲክታከሮች፣ ዩቱበሮች እና የኪነጥበብ ባለሙያዎች ዶክመንተሪ፣ ማስታወቂያ፣ ቀጥታ ሥርጭት መርሐግብሩን በትሩፋት በማገልገላቸው ከገዳሟ አበው መነኮሳት ማስታወሻ እንዲኾናቸው መንበሯ ላይ ያለችውን የድንግል ማርያም ሥዕለ አድኅኖ እና ሠርተፍኬት በስጦታ ተበርክቶላቸዋል።
ይኽንን ኹነት ከኮሚቴው ጋር በመተባበር የማስተባበር እና የማማከር ተግባር ለአንድ ወር ያከናወነው ሎዛ ኹነቶች - Liza Events በትሩፋት በማገልገሉ መንበሯ ላይ ያለችውን የድንግል ማርያም ሥዕለ አድኅኖ፣ የወርቅ ካባ እና ሠርተፍኬት ከብፁዕ አቡነ መቃርዮስ እና ከገዳሙ አበመኔት እጅ በስጦታ ተበርክቶለታል።
2 months ago
የእንጦጦ ኪዳነምሕረት የገቢ ማሰባሰቢያ
ሪከርድ በመስበር ተጠናቀቀ
ከመጋቢት 11 እሰ መጋቢት 12/2018 በእንጦጦ ኪዳነምሕረት አዳራሽ ሲከናወን የነበረው የገቢ ማሰባሰቢያ መርሐግብር 170,000,000.000 /አንድ መቶ ሰባ ሚሊያን/ ብር በመሰብሰብ ተጠናቀቀ።
ከዚኽ ውስጥ 139,000,000.00 ሚሊዬን ብር የተረጋገጠ ሲሆን ቀሪው 31 ሚሊዬ ብር ደግሞ ቃል የተገባ ሲሆን በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ ተጠናቆ ይገባል ተብሎ ይጠበቃል።
ይኽንን መሥሐግብር ብፁዕ አቡነ መቃርዮስ የምዕራብ ካናዳ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ መልአከ አሚን ቆሞስ አባ ገብረ ሥላሴ ይርሳው የገዳሟ ዋና አበመኔት፣ ማኅበረ መነኮሳቱ፣ ማኅበረ መነኮሳቱ፣ መምህራን፣ ዘማርያን፣ ምእመናን በሀገር ውስጥ እና በውጭ ሦስቱንም ሌሊት በንቃት ተሳትፈውበታል።
ቲክታከሮች፣ ዩቱበሮች እና የኪነጥበብ ባለሙያዎች ዶክመንተሪ፣ ማስታወቂያ፣ ቀጥታ ሥርጭት መርሐግብሩን በትሩፋት በማገልገላቸው ከገዳሟ አበው መነኮሳት ማስታወሻ እንዲኾናቸው መንበሯ ላይ ያለችውን የድንግል ማርያም ሥዕለ አድኅኖ እና ሠርተፍኬት በስጦታ ተበርክቶላቸዋል።
ይኽንን ኹነት ከኮሚቴው ጋር በመተባበር የማስተባበር እና የማማከር ተግባር ለአንድ ወር ያከናወነው ሎዛ ኹነቶች - Liza Events በትሩፋት በማገልገሉ መንበሯ ላይ ያለችውን የድንግል ማርያም ሥዕለ አድኅኖ፣ የወርቅ ካባ እና ሠርተፍኬት ከብፁዕ አቡነ መቃርዮስ እና ከገዳሙ አበመኔት እጅ በስጦታ ተበርክቶለታል።
ሪከርድ በመስበር ተጠናቀቀ
ከመጋቢት 11 እሰ መጋቢት 12/2018 በእንጦጦ ኪዳነምሕረት አዳራሽ ሲከናወን የነበረው የገቢ ማሰባሰቢያ መርሐግብር 170,000,000.000 /አንድ መቶ ሰባ ሚሊያን/ ብር በመሰብሰብ ተጠናቀቀ።
ከዚኽ ውስጥ 139,000,000.00 ሚሊዬን ብር የተረጋገጠ ሲሆን ቀሪው 31 ሚሊዬ ብር ደግሞ ቃል የተገባ ሲሆን በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ ተጠናቆ ይገባል ተብሎ ይጠበቃል።
ይኽንን መሥሐግብር ብፁዕ አቡነ መቃርዮስ የምዕራብ ካናዳ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ መልአከ አሚን ቆሞስ አባ ገብረ ሥላሴ ይርሳው የገዳሟ ዋና አበመኔት፣ ማኅበረ መነኮሳቱ፣ ማኅበረ መነኮሳቱ፣ መምህራን፣ ዘማርያን፣ ምእመናን በሀገር ውስጥ እና በውጭ ሦስቱንም ሌሊት በንቃት ተሳትፈውበታል።
ቲክታከሮች፣ ዩቱበሮች እና የኪነጥበብ ባለሙያዎች ዶክመንተሪ፣ ማስታወቂያ፣ ቀጥታ ሥርጭት መርሐግብሩን በትሩፋት በማገልገላቸው ከገዳሟ አበው መነኮሳት ማስታወሻ እንዲኾናቸው መንበሯ ላይ ያለችውን የድንግል ማርያም ሥዕለ አድኅኖ እና ሠርተፍኬት በስጦታ ተበርክቶላቸዋል።
ይኽንን ኹነት ከኮሚቴው ጋር በመተባበር የማስተባበር እና የማማከር ተግባር ለአንድ ወር ያከናወነው ሎዛ ኹነቶች - Liza Events በትሩፋት በማገልገሉ መንበሯ ላይ ያለችውን የድንግል ማርያም ሥዕለ አድኅኖ፣ የወርቅ ካባ እና ሠርተፍኬት ከብፁዕ አቡነ መቃርዮስ እና ከገዳሙ አበመኔት እጅ በስጦታ ተበርክቶለታል።
3 months ago
"የትወና ጌጥ" ምሽት!
አንጋፋ የኪነጥበብ ምሽት!
እባክዎ ሸር በማድረግ ተባበሩን!
47ኛው የባህል ማዕከል የኪነጥበብ ምሽት ረቡዕ መጋቢት 9፥2018 ዓ.ም ይካሄዳል።በዕለቱም ተወዳጇ ተዋናይት ሐረገወይን አሰፋ የክብር እንግዳችን ሆና በመካከላችን በመገኘት ሙያዊ ልምዷን ታካፍለናለች።
እንዲሁም ግጥሞች ፣ ወግ ፣ ሙዚቃና ሞኖሎግ ለእናንተ ውድ ታዳሚዎቻችንን በባህል ማዕከል አዳራሽ ከቀኑ በ 11: 30 ጀምሮ ተሰናድቶ ይጠብቃችኃል።
#ማስታወሻ :— ፕሮግራሙ ላይ ለመታደም የምትፈልጉ በአሁን ሰዓት የዩኒቨርስቲው ተማሪ ያልሆናችሁ የስነ-ጽሑፍ አፍቃሪያን መግቢያው በ5ተኛ በር በኩል ነው።
አንጋፋ የኪነጥበብ ምሽት!
እባክዎ ሸር በማድረግ ተባበሩን!
47ኛው የባህል ማዕከል የኪነጥበብ ምሽት ረቡዕ መጋቢት 9፥2018 ዓ.ም ይካሄዳል።በዕለቱም ተወዳጇ ተዋናይት ሐረገወይን አሰፋ የክብር እንግዳችን ሆና በመካከላችን በመገኘት ሙያዊ ልምዷን ታካፍለናለች።
እንዲሁም ግጥሞች ፣ ወግ ፣ ሙዚቃና ሞኖሎግ ለእናንተ ውድ ታዳሚዎቻችንን በባህል ማዕከል አዳራሽ ከቀኑ በ 11: 30 ጀምሮ ተሰናድቶ ይጠብቃችኃል።
#ማስታወሻ :— ፕሮግራሙ ላይ ለመታደም የምትፈልጉ በአሁን ሰዓት የዩኒቨርስቲው ተማሪ ያልሆናችሁ የስነ-ጽሑፍ አፍቃሪያን መግቢያው በ5ተኛ በር በኩል ነው።
Sponsored by
Surafel
3 months ago
የከተማ ይዞታን ለማስመለስ ክስ በይርጋ ይታገዳል?
(የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በሰባት ዳኞች በተሰጠ የህግ ትርጉም የተሰጠ የህግ ትንታኔ)
#ethiopia | በጠበቃና የህግ አማካሪ አልማው ወሌ የኢትዮጵያ ፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ከሰባት ያላነሱ ዳኞች የተሰየሙበት የሰበር ችሎት የካቲት 30 ቀን 2018 ዓ.ም በመ.ቁጥር 244308 የከተማ መሬት ይዞታን ለማስመለስ የሚቀርብ ክስ በይርጋ ይታገዳል ወይስ አይታገድም ? በሚለው አከራካሪ የህግ ነጥብ ላይ ሰበር ችሎቱ በሰጠው አስገዳጅ የሕግ ትርጉም ላይ የቀረበ አጭር ትንታኔ
የተከበሩ ጠበቃ እናመሠግናለን መልካም ንባብ
ኢትዮጵያ ፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ከሰባት ያላነሱ ዳኞች የተሰየሙበት የሰበር ችሎት የካቲት 30 ቀን 2018 ዓ.ም በመ.ቁጥር 244308 ላይ በሰጠው አስገዳጅ የሕግ ትርጉም ላይ የቀረበ አጭር ትንታኔ 1
ክፍል አንድ፡ መግቢያ እና የሥነ-ሥርዓት ዳራ 1
ክፍል ሁለት፡ የሦስቱ ቀደምት አስገዳጅ ውሳኔዎች አጠቃላይ ትንታኔ 1
ክፍል አራት፡ የሰባት ዳኞች ችሎት አዲሱ የሕግ ትርጉም 3
ክፍል አምስት፡ ተግባራዊ የተደረጉት የፍትሐብሔር ሕግ ድንጋጌዎች ትንታኔ 4
ክፍል ስድስት፡ ስለ አዲሱ ትርጉም ጥንካሬዎች 4
ክፍል ሰባት፡ የውሳኔው ማጠቃለያ እና ቀጣይ አንድምታዎች 4
7.1 አዲሱን ሕግ በመታየት ላይ ባሉ ጉዳዮች ላይ ያለመተግበር ትክክለኛነት፡ የሽግግር ድንጋጌዎችን በጥብቅ መከተል 5
7.2 የአመሳስሎሽ ትርጓሜ ችግር፡ የሕግ ክፍተትን ለመሙላት በተመረጠው ምንጭ ላይ የታየ የፅንሰ-ሐሳብ (የዶክትሪን) መዛባት 6
7.3 የክፍል 7 ጥማቂ 8
ክፍል ስምንት፡ አጠቃላይ ግምገማ 9
የኢትዮጵያ ፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ከሰባት ያላነሱ ዳኞች የተሰየሙበት የሰበር ችሎት የካቲት 30 ቀን 2018 ዓ.ም በመ.ቁጥር 244308 ላይ በሰጠው አስገዳጅ የሕግ ትርጉም ላይ የቀረበ አጭር ትንታኔ
ክፍል አንድ፡ መግቢያ እና የሥነ-ሥርዓት ዳራ
ከሰባት ያላነሱ ዳኞች የተሰየሙበት የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት የካቲት 30 ቀን 2018 ዓ.ም. የሰጠው ይህ ውሳኔ በመ/ቁጥር 210477 ላይ ተሰጥቶ የነበረውን አስገዳጅ የህግ ትርጉም በመለወጥ ተሰጠው (Overruling) ውሳኔ ሲሆን በአገሪቱ የንብረት ሕግ ስነ ህግ እድገት እና በአስገዳጅ የህግ ትርጉም ስርዓት ላይ የራሱ የሆነ አንድምታ ያለው መሆኑ ይታመናል፡፡ ይህ አዲስ አስገዳጅ የህግ ትርጉም ለውጥ በችሎቱ የተሰጠው በፌዴራል ፍርድ ቤቶች አዋጅ ቁጥር 1234/2013 አንቀጽ 26(1) ድንጋጌ እና በሰበር ስነ ስርዓት መመሪያ ቁጥር 17/2015 አንቀፅ 14(2) በተዘረጋው ስርዓት ሲሆን ችሎቱ የተሰየመበትም ዋነኛ ምክንያትም የከተማ መሬት ይዞታን ለማስመለስ የሚቀርብ ክስ በይርጋ ይታገዳል ወይስ አይታገድም ? በሚለው አከራካሪ የህግ ነጥብ ላይ ሰበር ችሎቱ ቀደም ሲል በሰጣቸው አስገዳጅ ውሳኔዎች መካከል ሊታረቅ የማይችል ተቃርኖ በመፈጠሩ ነው፡፡ የጉዳዩ ምንጭ አቶ ጅላሎ ኩመል ሼህረዲ (አመልካች/ተከሳሽ) እና አቶ ታምራት መርከቡ ፍልቾ (ተጠሪ/ከሳሽ) በአዲስ አበባ ከተማ (ለሚ ኩራ ክፍለ-ከተማ፣ ወረዳ 08፣ ፊጋ ሰፈር በሚባል አካባቢ) በሚገኝ 2,000 ካሬ ሜትር የከተማ ቦታ ላይ ያደረጉት ክርክር ነው፡፡ ጉዳዩ ለሰባት ዳኞች ችሎት መመራቱ ሥነ-ሥርዓታዊ ሂደት ብቻ ሳይሆን ጥልቅ መሠረታዊ የሕግ ይዘት ያለው ጉዳይ ሲሆን ችሎቱም በሕግ አተገባበር ላይ ወጥነት እና ተገማችነትን የማረጋገጥ ኃላፊነቱን ለመውጣት በተጠቃሽ ውሳኔዎቹ መካከል የታየውን ተቃርኖ አስታራቂ እና ግልጽ አቋም ሊያዝበት የሚገባ መሆኑን በግልጽ አስፍሯል፡፡ ይህ እርስ በእርሱ የሚቃረኑ አስገዳጅ ውሳኔዎች ሥርዓታዊ የሆነ ችግር እንዳያስከትሉ ችሎቱ ራሱን በራሱ በማረም የወሰደው ዕርምጃ በኢትዮጵያ የአስገዳጅ የህግ ትርጉም ሥርዓት ውስጥ ያለውን ተቋማዊ ብስለት የሚያሳይ ነው ተብሎ ሊወሰድ የሚገባው ነው፡፡
ክፍል ሁለት፡ የሦስቱ ቀደምት አስገዳጅ ውሳኔዎች አጠቃላይ ትንታኔ
በመጀመሪያ ደረጃ በሰበር መዝገብ ቁጥር 43600 ጥር 05 ቀን 2002 ዓ.ም. የተወሰነውንና በቅጽ 10 የታተመውን አስገዳጅ የህግ ትርጉም በአጭሩ ስንመለከት ጉዳዩ አቶ ዳዊት መስፍን ከተጠሪ የመንግስት ቤቶች ኤጀንሲ ጋር ያደረጉት ክርክር ነበር፡፡ አቶ ዳዊት በአዲስ አበባ ከተማ (የቀድሞ ወረዳ 118፣ ቀበሌ 05) የሚገኝ መኖሪያ ቤት የባለቤትነት መብትን መሠረት በማድረግ ቤቱ እንዲለቀቅላቸው ክስ አቅርበው ነበር፡፡ ለዚህም በጥቅምት 23 ቀን 1985 ዓ.ም. የተሰጠ የከተማ ቤት ባለቤትነት ማረጋገጫ ደብተር አቅርበዋል፡፡ ተጠሪው (ኤጀንሲው) በበኩሉ፣ የፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 1845ን ማለትም የ10 ዓመቱን የውል ግዴታዎች ይርጋ ድንጋጌ በመጥቀስ የይርጋ መቃወሚያ አቅርቦ ነበር፡፡ የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት እና የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የይርጋ መቃወሚያውን በመቀበል ክሱን ውድቅ አድርገውት ነበር፡፡ ጉዳዩ የቀረበለት የሰበር ችሎት ግን የማይንቀሳቀስ ንብረትን በተመለከተ የሚቀርብ የመፋለም ክስ በይርጋ ቀሪ የሚሆንበት አግባብ መኖር አለመኖሩን ጭብጥ አድርጎ በመያዝ ጥልቅ ትንታኔ ሰጥቷል፡፡ የሰበር ችሎቱ ትንታኔውን የጀመረው ማናቸውም ኢትዮጵያዊ የንብረት ባለቤት መሆኑ በሕገ-መንግስቱ አንቀጽ 40(1) የተረጋገጠ መሆኑን በማንሳት ሲሆን፣ በመቀጠልም የፍትሐብሔር ሕጉን የንብረት ድንጋጌዎች ማለትም አንቀጽ 1126፣ 1168፣ 1184፣ እና 1186 ደንጋጌዎችን እንዲሁም በፍ/ህ/ቁጥር 1188 እስከ 1192 ድረስ ያሉትን ድንጋጌዎችን ሙሉ ይዘትና መንፈስ በዝርዝር ተመልክቷል፡፡ ችሎቱ ወሳኝ ብሎ ያነሳው ነጥብ የፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 1192 "ባለሀብትነትን የሚያስቀር የይርጋ ዘመን" ብሎ ያስቀመጠው ለሚንቀሳቀስ ንብረት ብቻ መሆኑን እና ስለ ማይንቀሳቀስ ንብረት በዝምታ ማለፉን ነው፡፡ ከዚህም በተጨማሪ በአንቀጽ 1206 ሥር የተደነገገው የመፋለም ክስ የባለቤትነት መብት ከሁሉ የሰፋ መብት መገለጫ መሆኑን፣ እና የማይንቀሳቀስ ንብረት ባለቤትነት ዘላቂነት (Perpetuity) ያለው መብት በመሆኑ በይርጋ ቀሪ እንዳይሆን የሕግ አውጪው ፍላጎት መሆኑን አብራርቷል፡፡ በዚህም መሠረት የፍ/ብ/ሕ/ቁ 1845 ድንጋጌን ተፈፃሚ ማድረግ የሕጉን አወቃቀርና መንፈስ የሚያፋልስ መሆኑን በመግለጽ፣ የማይንቀሳቀስ ንብረት የመፋለም መብት ክስ በይርጋ ቀሪ አይሆንም ወደሚል ድምዳሜ ደርሷል፡፡ ይህ ውሳኔ በፅንሰ-ሐሳብ ደረጃ ጠንካራ ቢሆንም፣ ዋነኛ ክፍተቱ ትንታኔው ሙሉ በሙሉ ታሳቢ ያደረገው "የግል ባለቤትነት መብት" (Private Ownership) መኖርን መሆኑ ነው፡፡ ጉዳዩ መኖሪያ ቤትን የሚመለከት ስለነበር ይህ አካሄድ ትክክል ቢሆንም፣ የባለቤትነት መብት በሕገ-መንግሥት በተከለከለበት መሬት ላይ ትንታኔው እንዴት ሊተገበር ይችላል ለሚለው ጥያቄ ምላሽ የሚሰጥ አልነበረም፡፡ ሆኖም ትርጉም በሌሎች ልዩ ህጎች ያሉትን የይርጋ ድንጋጌዎችን የማይነካ መሆኑ በማሳሳብ አልፏል፡፡
በሁለተኛ ደረጃ በሰ/መ/ቁጥ 69302 ታህሳስ 20 ቀን 2004 ዓ.ም. የተሰጠውን አስገዳጅ የህግ ትርጉም ስንመለከት፦ ጉዳዩ በአመልካች አቶ ሸለማ ነገሰ እና በተጠሪ አቶ ፋይሣ መንግስቱ መካከል በኦሮሚያ ክልል፣ ኖኖ ቤንጃ ወረዳ በሚገኝ የገጠር እርሻ መሬት ላይ የተደረገ ክርክር ነው፡፡ ተጠሪ አባቴ በሞት ከተለየበትמ 1985 ዓ.ም.
ጀምሮ አመልካች መሬቱን አላግባብ ስለያዘብኝ ይልቀቅልኝ ሲል ክስ ያቀረበ ሲሆን አመልካች በበኩሉ መሬቱን ለ18 ዓመታት መያዙን በመግለጽ ተከራክሯል፡፡ የስር ፍርድ ቤቶች መሬቱ እንዲለቀቅ የወሰኑ ቢሆንም የሰበር ችሎቱ ግን አርሶ አደሮች የእርሻ መሬት የማግኘትና ያለመፈናቀል መብት እንዳላቸው ሕገ-መንግሥቱ በአንቀጽ 40(4) መሠረት ማረጋገጡን ጠቅሶ፣ ይሁን እንጂ መሬቱን በሌላ ሰው የተነጠቀ አርሶ አደር ክስ ማቅረብ ስላለበት የጊዜ ገደብ የገጠር መሬት አዋጆች በግልጽ አለመደንገጋቸውን በማንሳት የሕግ ክፍተት መኖሩን አሳይቷል፡፡ የፍትሐብሔር ሕጉ የሁከት ይወገድልኝ ክስ የ2 ዓመት ይርጋን (አንቀጽ 1149(2)) መተግበር የአርሶ አደሩን ሕገ-መንግሥታዊ መብት አጥብቦ የሚገድብ በመሆኑ ውድቅ በማድረግ፣ በፍ/ብ/ሕ/ቁ 1677(1) ስር የተመለከተውን ድንጋጌ እንደ ድልድይ በዋቢነት በመጥቀስ የፍ/ብ/ሕ/ቁ 1845 የ10 ዓመት ይርጋ በገጠር መሬት ይዞታ ላይ ተግባራዊ እንዲሆን ወስኗል፡፡ ይህ ውሳኔ ምንም እንኳን ከመዝገብ ቁጥር 43600 ፈጽሞ የተለየ አቀራረብ ይዞ የመሬት ይዞታን ከባለቤትነት መብት ነጥሎ በማየት የ10 ዓመት ይርጋ ተግባራዊ ያደረገ ቢሆንም፣ የውል ድንጋጌ የሆነውን የፍ/ህ/ቁ 1845 ድንጋጌን በቀጥታ መሬት ላይ ለመተግበር የሄደበት መንገድ በበቂ ሁኔታ ያልተብራራ መሆኑ እንደ ሂሳዊ ድክመት ሊነሳበት ይችላል፡፡
በሦስተኛ ደረጃ በሰ/መ/ቁ 210477 ታህሳስ 27 ቀን 2014 ዓ.ም. የተወሰነውንና አሁን የተሻረውን ስንመለከት፣ ጉዳዩ በአዲስ አበባ ከተማ ቦሌ ክፍለ-ከተማ ውስጥ የሚገኝ የከተማ መሬት ይዞታን በተመለከተ በአመልካቾች (የአቶ ነጋሳ ዱቤ ወራሾች) እና በተጠሪዎች (ወ/ሮ ጸሐይ ቹቾ እና ወ/ሮ ሴደሬ ንጉሴ) መካከል የተደረገ ክርክር ነበር፡፡ ተጠሪዎች ቦታውን ከ1993 ዓ.ም. ጀምሮ ለ19 ዓመታት መያዛቸውን በመግለጽ የይርጋ መቃወሚያ አቅርበው የስር ፍርድ ቤቶችም መቃወሚያውን ተቀብለውት ነበር፡፡ ሆኖም የሰበር ችሎቱ ይህንን ውሳኔ በመሻር፣ የቀረበው ክስ "የመፋለም ክስ" መሆኑን በመግለጽ የቤትን ባለቤትነት የተመለከተውን የሰ/መ/ቁ 43600 አመክንዮ በቀጥታ በመዋስ "የከተማ መሬት ይዞታን በተመለከተ የሚቀርብ የመፋለም ክስ በይርጋ አይታገድም" የሚል አስገዳጅ ትርጉም ሰጥቶ ነበር፡፡ የዚህ ውሳኔ ዋነኛ ስህተት የባለቤትነት መብትን (Ownership) እና የይዞታ መብትን (Holding rights) አንድ አድርጎ ማየት መቻሉ ነው፡፡ ሕገ-መንግሥቱ በአንቀጽ 40(3) መሠረት ግለሰቦች በመሬት ላይ የባለቤትነት መብት እንደሌላቸው እየደነገገ፣ በሰ/መ/ቁ 210477 የተሰጠው አስገዳጅ የህግ ትርጉም ግን የባለቤትነት መብት ጥበቃን (ከይርጋ ነፃ መሆንን) በመሬት ይዞታ መብት ላይ በመተግበሩ መሠረታዊ የሆነ የፅንሰ-ሐሳብ እና የሕግ ስህተት ተፈጽሞበት የነበረ ጉዳይ ነው፡፡
ክፍል ሦስት፡ በውሳኔዎቹ መካከል የነበረው ተቃርኖ እና የሕግ ማዕቀፎች
በእነዚህ ሦስት ውሳኔዎች መካከል የተፈጠረው ተቃርኖ እጅግ የጎላ እንደነበር በቀላሉ መገንዘብ ይቻላል፡፡ በአንድ በኩል መዝገብ ቁጥር 43600 በቤት ባለቤትነት ላይ የመፋለም ክስ ይርጋ የለውም ሲል፣ በሌላ በኩል በሰ/መ/ቁ 69302 በገጠር መሬት ይዞታ ላይ የ10 ዓመት ይርጋ ተፈፃሚ አድርጓል፡፡ በተቃራኒው ደግሞ በሰ/መ/ቁ 210477 የከተማ መሬት ይዞታን አስመልክቶ የቀረበን ክርክር የባለቤትነት ጉዳይ ከሆነው ከሰ/መ/ቁ 43600 ጋር በማመሳሰል የከተማ መሬት ክስ በይርጋ አይታገድም በማለት ወስኗል፡፡ ይህ ሁኔታ በመሬት ይዞታዎች (በገጠር እና በከተማ) ላይ የተለያየ እና ምክንያታዊ ያልሆነ የይርጋ አተገባበር እንዲፈጠር አድርጎ የነበረ መሆኑ ከውሳኔዎቹ በግልፅ ይታያል፡፡
ይህንን ተቃርኖ ለመፍታት የሰባት ዳኞች ችሎት በርካታ ሕጎችን አንድ ላይ መመርመር ነበረበት፡፡ ከእነዚህም ውስጥ የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ሕገ-መንግሥት አንቀጽ 40(3) ስለ መሬት የመንግስትና የሕዝብ ንብረትነት፣ አንቀጽ 40(4) ስለ አርሶ አደሮች መብት፣ እና አንቀጽ 40(7) በጉልበትና በገንዘብ ስለሚፈራ ንብረት ያካተቱት ድንጋጌዎች ይገኙበታል፡፡ በተጨማሪም የፍትሐብሔር ሕግ አንቀጽ 1192፣ አንቀጽ 1206 (ስለ መፋለም ክስ)፣ አንቀጽ 1149(2) (የሁከት ክስ ይርጋ)፣ እንዲሁም አንቀጽ 1677(2) እና 1845 ድንጋጌዎች ሙሉ ይዘታቸው ተፈትሸዋል፡፡ ከእነዚህ በተጨማሪም የከተማ ቦታ በሊዝ ስለመያዝ የወጣው አዋጅ ቁጥር 721/2004፣ የከተማ መሬት ይዞታ ምዝገባ አዋጅ ቁጥር 818/2006 እና የገጠር መሬት አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 1324/2016 አግባብነት ያላቸው የሕግ ማዕቀፎች በመሆናቸው በችሎቱ ታሳቢ ተደርገዋል፡፡
ክፍል አራት፡ የሰባት ዳኞች ችሎት አዲሱ የሕግ ትርጉም
ሰባት ዳኞች የተሰየሙበት የሰበር ችሎት ይህንን የተወሳሰበ የሕግ ጥያቄ ለመፍታት የተጠቀሱትን ቀደምት አስገዳጅ ውሳኔዎችን በመመርመር ለእያንዳንዳቸው ተገቢ ነው ያለውን ማብራሪ ሰጥቶባቸዋል፡፡ በመጀመሪያ በሰ/መ/ቁጥር 43600 የተሰጠውን አስገዳጅ የህግ ትርጉምን አልሻረውም፤ ይልቁንም ጉዳዩ መኖሪያ ቤትን የሚመለከት በመሆኑና መኖሪያ ቤት ላይ የባለቤትነት መብት ስላለ፣ ትንታኔው ከዚህ መዝገብ ጋር በቀጥታ እንደማይገናኝ በማስረዳት የጉዳዩን ልዩነት (Distinguishing) በማሳየት ትርጉሙ እንዲፀና አድርጎታል፡፡ በመቀጠልም በሰ/መ/ቁጥር 69302 ለገጠር መሬት የተሰጠውን የ10 ዓመት ይርጋ አስገዳጅ የህግ ትርጉም ትክክለኛነት የተቀበለ ቢሆንም፣ ይህንን የገጠር መሬት ቀደመት አስገዳጅ ትርጉም በቀጥታ በከተማ መሬት ላይ መተግበሩ ስህተት መሆኑን በማሳየት የስር ፍርድ ቤትን አካሄድ ነቅፏል፡፡ በመጨረሻም በሰ/መ/ቁጥር 210477 የተሰጠውን አስገዳጅ የህግ ትርጉም ሙሉ በሙሉ የሻረው ሲሆን ለውሳው ምሶሶ ያደረጋቸው አበይት ምክንያቶቹም የቀደመው አስገዳጅ የህግ ትርጉም የባለቤትነት መብትን እና የይዞታ መብትን በማምታታት፣ በመሬት ይዞታ መብት ላይ ሊቀርብ የማይችለውን የመፋለም ክስ የይርጋ መቃወሚያ በከተማ መሬት ይዞታ ላይ ተግባራዊ ማድረግ አይቻልም የሚሉት መሆናቸውን አዲሱ ትርጉም በግልጽ አስቀምጧል፡፡
ችሎቱ አዲሱን የሕግ ትርጉም ለመስጠትና ለመተንተን የተከተለው አመክንዮ አራት ደረጃዎችን ያካተተ ነበር፡፡ አንደኛ ትንታኔውን በሕገ-መንግስቱ አንቀጽ 40(3) ላይ በማስረፅ መሬት የግለሰብ ባለቤትነት ሊኖርበት የማይችል መሆኑን እና የፍ/ብ/ሕ/ቁ 1206 የመፋለም ክስ መሬት ላይ ተፈፃሚ እንደማይሆን አረጋግጧል፡፡ ሁለተኛ በከተማ መሬት ይዞታ ላይ የሚኖረው መብት (በሊዝም ሆነ በነባር) በነገር ላይ ያለ (In rem) ተጨባጭ የንብረት መብት እንጂ ተራ የኪራይ ውል ግንኙነት አለመሆኑን በማብራራት የመብቱን ህልውና ገልጿል፡፡ ሦስተኛ የሲቪል ሎው (Civil Law) የመፋለም ክስ ፅንሰ-ሐሳብ እና የኮመን ሎው (Common Law) የማስለቀቅ ክስ (Action of ejectment) ፅንሰ-ሐሳቦችን በማነፃፀር፣ ምንም እንኳን ይህ የኮመን ሎው አሠራር ለሕግ ሥርዓታችን እንግዳ ቢሆንም፣ በሕግ የታወቀ መብት እስካለ ድረስ ስያሜው ክሱን ለማስተናገድ እክል እንደማይሆን አብራርቷል፡፡ አራተኛ የሕግ ክፍተቱን ለመሙላት (Gap-filling) የፍ/ብ/ሕ/ቁ 1677(2) ድንጋጌን ድልድይ በማድረግ በፍ/ብ/ሕ/ቁ 1845 ሥር የተቀመጠውን አጠቃላይ የ10 ዓመት ይርጋ በከተማ መሬት ይዞታ ላይ ተግባራዊ አድርጓል፡፡ በዚህም መሠረት
የከተማ መሬት ይዞታን አላግባብ ከያዘ ሰው ላይ ለማስመለስ የሚቀርብ ክስ በአስር ዓመት ይርጋ ይታገዳል የሚል አዲስ አስገዳጅ የሕግ ትርጉም ሰጥቷል፡፡
ክፍል አምስት፡ ተግባራዊ የተደረጉት የፍትሐብሔር ሕግ ድንጋጌዎች ትንታኔ
በዚህ ውሳኔ ተግባራዊ የተደረገው የፍ/ህ/ቁ 1845 "በውል ስለሚመነጩ ግዴታዎች" ሥር የሚገኝ ሲሆን፣ ውልን ስለመፈፀም፣ ባለመፈፀም እና ውልን ስለማፍረስ የሚቀርቡ ክሶች በአስር ዓመት ይርጋ እንደሚታገዱ የሚደነግግ ነው፡፡ የመሬት ይዞታ ክርክር ደግሞ በባህሪው ከውል የሚመነጭ ሳይሆን ከሕገ-ወጥ ይዞታ ወይም ንጥቂያ የሚመነጭ ነው፡፡ ሆኖም ችሎቱ ይህንን ክፍተት ያገናኘው የፍ/ብ/ሕ/ቁ 1677(2) ድንጋጌን በዋቢነት በመጥቀስ ሲሆን ይህ ድንጋጌ የውል ደንቦች ከውል ውጭ በሆኑ ግዴታዎች ላይ ተፈፃሚ እንደሚሆኑ ይደነግጋል፡፡ ይሁን እንጂ ሕገ-ወጥ የመሬት ያዥ ያለበት "ግዴታ" ምን ዓይነት እንደሆነ (ከሕገ-ወጥ ድርጊት ወይስ ያለአግባብ ከመበልፀግ የመነጨ መሆኑን) ችሎቱ በግልጽ አላብራራም፡፡ እንዲሁም በፍ/ህ/ቁ 1846 መሠረት የይርጋው መቆጠር መነሻ ጊዜ ከመቼ እንደሚጀምር፣ በአንቀጽ 1851 መሠረት የይርጋ መቋረጥ እንዴት እንደሚስተናገድ፣ እና በፍ/ህ/ቁጥር 1854 መሠረት መጥፎ ልቦና (Bad faith) ያለው ሰው እንኳን በይርጋው መጠቀም የሚችል መሆኑ በመሬት ንጥቂያ ላይ የሚያመጣው ህጋዊ ውጤት/ ተፅዕኖ መኖር ያለመኖሩን በችሎቱ ትንታኔ ሥር በሰፊው ያልተዳሰሱ ግን መሰረታዊ የሆኑ የህግ ጥያቄዎች ሆነው አልፈዋል፡፡
ክፍል ስድስት፡ ስለ አዲሱ ትርጉም ጥንካሬዎች
የሰባት ዳኞች ችሎት የሰጠው ይህ ውሳኔ በኢትዮጵያ የንብረት ሕግ ስነ ህግ ዕድገት ላይ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ያላቸው በርካታ ጥንካሬዎችን ይዟል፡፡ በመጀመሪያ ደረጃ ችሎቱ የፍትሐብሔር ሕጉን እና የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ሕገ-መንግሥትን የመሬት መብት ስሪት በአግባቡ በማዋሃድ የግል ባለቤትነትን እና የመሬት ይዞታ መብትን በጥልቀት ለመለየት መቻሉ ሊደነቅ የሚገባው ሕገ-መንግሥታዊ ትንታኔ ነው፡፡ በተጨማሪም በሰ/መ/ቁጥር 43600 የተሰጠውን አስገዳጅ የህግ ትርጉምን ሙሉ በሙሉ ከመሻር ይልቅ በሚገባው የሕግ አውድ (በቤት ባለቤትነት ላይ) ብቻ እንዲወሰን በማድረግ ትክክለኛ የአስገዳጅ የህግ ትርጉም አስተዳደር/አተገባበርን ለማሳየት ችሏል፡፡ እንዲሁም የባለቤትነትን እና የይዞታ መብትን ማምታታት በሰ/መ/ቁጥር 210477 የተሰጠውን መሠረታዊ የሕግ ስህተት ያለበትን አስገዳጅ የህግ ትርጉም በአግባቡ በማረም ለአስገዳጅ የሕግ ትርጉም ስርዓት ጥራት እና ታዓማኒነት አስተዋጽኦ አድርጓል፡፡ ችሎቱ የከተማ መሬት መብቶችን ተራ የውል ግንኙነት ሳያደርግ ከሁሉም ሰዎች ልንጠይቃቸው የምንችላቸው ተጨባጭ መብቶች (In rem) መሆናቸውን ማረጋገጡ እና ጉዳዩን በ7 ዳኞች በማየት ተቋማዊ ቅቡልነትነን (Institutional Legitimacy) ማጠናከሩ የውሳኔው ዐበይት ጥንካሬዎች ናቸው፡፡
ክፍል ሰባት፡ አዲሱ አስገዳጅ የሰበር ውሳኔ እና አዋጅ ቁጥር 1324/2016፡ የሕግ በጊዜ አተገባበር እና የአመሳስሎሽ ትርጓሜ መነጽር የተደረገ ዳሰሳ
7.1 መግቢያ
የካቲት 30 ቀን 2018 ዓ.ም. ሰባት ዳኞች በተሰየሙበት የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት የተሰጠው አስገዳጅ ውሳኔ ቁልፍ ትርጉሙ (Ratio decidendi)፤ የከተማ መሬት ይዞታን ሕገ-ወጥ ከሆነ መንገድ ከያዘው ሰው ላይ ለማስመለስ የሚቀርብ ክስ በ10 ዓመት ይርጋ ይታገዳል የሚለው ሲሆን ፣ "የሕግ በጊዜ አተገባበር" (Intertemporal law፤ ሕጎች በጊዜ ሂደት ያላቸውን ተፈፃሚነት የሚገዛ መርህ) እና "የአመሳስሎሽ ትርጓሜ" (Analogical reasoning) ተቀራራቢ የሕግ ድንጋጌዎችን በመጠቀም የሕግ ክፍተትን የመሙላት ሥነ-ዘዴ) በሚሉት ሁለት መነጽሮች ሲመረመር እጅግ አሳማኝ የሆኑ አካዳሚያዊ እና ተግባራዊ ጥያቄዎችን ሊስነሳ የሚችል ነው፡፡ ይህ አዲስ አስገዳጅ ውሳኔ እና ከእርሱ በፊት ነሐሴ 8 ቀን 2016 ዓ.ም የወጣው የፌዴራል የገጠር መሬት አስተዳደርና አጠቃቀም አዋጅ ቁጥር 1324/2016. መገጣጠም፣ የችሎቱን ሥነ-ሥርዓታዊ ትክክለኛነት እና የፅንሰ-ሐሳብ (የዶክትሪን) ምርጫዎች ለየብቻ እና በሂሳዊ መንገድ እንድንገመግም ሰፊ የትንታኔ መደላድል የሚፈጥር ይመስለኛል፡፡ በዚህ ረገድ ሊደረግ የሚችለው ትንታኔ የጉዳዩን ፍሬ-ነገሮች፣ የአዋጅ ቁጥር 1324/2016 ድንጋጌ አግባብነት ያላቸውን ድንጋጌዎች (በተለይም የይርጋ እና የሽግግር ድንጋጌዎችን)፣ እና የፍትሐብሔር ሕጉን የይርጋ ማዕቀፍ መሠረት በማድረግ ሊከናወን የሚችል ነው፡፡
በሌላ በኩል ውሳኔው አንዳንድ ድክመቶች እና ቀጣይ ማብራሪያ የሚሹ ክፍተቶችም የሚታዩበት መሆኑን የግል ምልክታ አድርጌአለሁ፡፡ የፍ/ብ/ሕ/ቁ 1845 የ10 ዓመት ይርጋ በከተማ መሬት ላይ ተግባራዊ እንዲሆን የተሰጠው ትንታኔ አጠር ያለ እና ተጨማሪ ማብራሪያ የሚሻ ነው፡፡ ይህንን ይርጋ ተግባራዊ ማድረግ በተለይም ከአገር ውጭ በነበሩ ወይም በተለያዩ አቅም በሚያሳጡ ሁኔታዎች ውስጥ ላሉ ዜጎች ሕገ-መንግሥታዊ መብት ላይ የሚያመጣው ተፅዕኖ ከፖሊሲ አኳያ አልተገመገመም፡፡ እንዲሁም በሰ/መ/ቁጥር 43600 የተሰጠውን የህግ ትርጉምን በተመለከተ "ተፈፃሚ ለማድረግም ሆነ ተቃርኖ አለው ለማለት አልተቻለም" የሚለው የችሎቱ አገላለጽ የተወሰነ ብዥታን የሚፈጥርና ይበልጥ ግልጽ ቢደረግ ይመረጥ የነበረ ነው፡፡ በዚሁ አስገዳጅ ውሳኔ ውስጥ በሌሎች ልዩ ህጎች የተመለከቱትን የይርጋ ድንጋጌዎችን በሚመለከት የተቀመጠውን አገላለፅ መጠቀም ያልተቻለበትን አግባብ ውሳኔው አያሳይም፡፡ ከዚህም በተጨማሪ የመፋለም ክስ ከመሬት ጋር እንደማይሄድ ከተገለጸ በኋላ፣ በትክክል ክሱ በምን ዓይነት የክስ ምክንያት (Cause of action) መቅረብ እንዳለበት ግልጽ አቅጣጫ አለመቀመጡ ለባለሙያዎች ክፍተት ትቷል፡፡ ከገጠር መሬት አዋጅ ድንጋጌዎች ጋር በማነፃፀር ለከተማ መሬት ተመሳስሎሽ ትንታኔ (Analogical reasoning) ያልተጠቀመበትን አግባብም መኖሩን ውሳኔው ማሳየቱን ችሎቱ እንዲህ አይነት የህግ ትርጉም ስልት ተግባር ላይ ለማዋል/ለመውሰድ የነበረውን መልካም አጋጣሚ ማምከኑን የሚያሳይ ነው፡፡ እንዲሁም ቅን ልቦ የሌለው ወይም መጥፎ ልቦና (Bad faith) ያለው የመሬት ነጣቂ የ10 ዓመት ይርጋን ተገን አድርጎ መብት ሊያገኝ የሚችልበትን የፍ/ህ/ቁጥር 1854 ድንጋጌ አንድምታ ችሎቱ አለመመርመሩ እንደ ውሳኔው ድክመቶች ሊነሱ የሚችሉ ነጥቦች ይመስሉኛል፡፡
7.2 አዲሱን ሕግ በመታየት ላይ ባሉ ጉዳዮች ላይ ያለመተግበር ትክክለኛነት፡ የሽግግር ድንጋጌዎችን በጥብቅ መከተል
ከላይ እንደተጠቀሰው በፍ/ብ/ህ/ሥ/ሥርዓት እና በሕግ ትርጓሜ መሠረታዊ መርሆች መሠረት፣ አዲስ የወጣ መሰረታዊ ሕግ (Substantive law) የሕግ አውጪው በግልጽ ካልደነገገ በስተቀር ወደኋላ ተመልሶ አይሰራም፡፡ ይህ ሕግ ወደኋላ ተመልሶ አለመሥራት መርህ (lex prospicit, non respicit) የሕግ ተገማችነት (Legal certainty) የጀርባ አጥንት ሲሆን፣ የተከራካሪ ወገኖች መብት እና ግዴታ የሚገዛው ድርጊቱ በተፈጸመበት ወይም ቢያንስ ክርክሩ በፍርድ ቤት በተጀመረበት ጊዜ በነበረው ሕግ መሆኑን ያረጋግጣል፡፡ አሁን በተያዘው ጉዳይ ይህ መርህ እጅግ ግልጽ በሆነ መንገድ ይሠራል፡፡ ተጠሪ (ከሳሽ) ክሳቸውን ያቀረቡት ሐምሌ 14 ቀን 2013 ዓ.ም.
ሲሆን፣ የክሱ መነሻ (ሕገ-ወጥ የመሬት ይዞታ ንጥቂያ) ተከሰተ የተባለው ደግሞ በ2011 ዓ.ም. (ወይም አመልካች እንደሚሉት በ1980 ዓ.ም.) ነው፡፡ በአንፃሩ አዲሱ የገጠር መሬት አስተዳደርና አጠቃቀም አዋጅ ቁጥር 1324/2016 ፀድቆ በነጋሪት ጋዜጣ ታትሞ የወጣው በነሐሴ 08 ቀን 2016 ዓ.ም. ነው፡፡ ይህም ማለት ክርክሩ ከተጀመረና በተለያዩ የፍርድ ቤት እርከኖች ሲንከባለል ከቆየ ከዓመታት በኋላ ነው፡፡ ዋናው ቁም ነገር አዋጁ ራሱ ይህንኑ ሁኔታ የሚገዛ ግልጽ የሽግግር ድንጋጌ (Transitional provision) የያዘ መሆኑ ነው፡፡ የአዋጅ ቁጥር 1324/2016 አንቀጽ 65(1) በማያሻማ ቋንቋ እንዲህ ይደነግጋል፡- "የዚህ ሕግ ድንጋጌዎች ይህ አዋጅ ከመፅደቁ በፊት… ፍርድ ቤት ቀርበው ክርክር እየተደረገባቸው ባሉ ጉዳዮች ላይ ተፈፃሚ አይሆንም"፡፡ ይህ ድንጋጌ አዲሱ ሕግ፤ በአዋጁ የተካተቱ ማናቸውንም የይርጋ ጊዜያት ጨምሮ፣ ወደፊት ብቻ የሚሠራ እንጂ አዋጁ ከመውጣቱ በፊት በፍርድ ቤት በመታየት ላይ የነበሩ ጉዳዮችን ወደኋላ ተመልሶ እንደማያካትት የሕግ አውጪው የሰጠው ግልጽ መመሪያ ነው፡፡
ይህ የሽግግር ድንጋጌ በቀጥታ አግባብነት ያለው፣ የዚሁ አዋጅ አንቀጽ 64(2) ለመሬት ማስለቀቅ ክስ የ15 ዓመት የይርጋ ጊዜ ስለሚደነግግ ነው፡፡ ይህ ድንጋጌ ለዚህ ጉዳይ ተፈፃሚነት ቢኖረው ኖሮ ውጤቱን ሊቀይረው ይችል ነበር፡- ማለትም ፍርድ ቤቱ በተገበረው የ10 ዓመት ይርጋ ታግዷል የተባለው የተጠሪ ክስ፣ የይርጋው መቆጠር መነሻ ጊዜ አሰላል ታይቶ በ15 ዓመቱ የይርጋ ጊዜ ሥር ሊድን (ሊቀጥል) ይችል ነበር፡፡ ሆኖም ሰባት ዳኞች የተሰየሙበት የሰበር ችሎት ይህንን አዲስ የ15 ዓመት የይርጋ ጊዜ ከ2013 ዓ.ም. ጀምሮ በፍርድ ቤት በመታየት ላይ ባለ ጉዳይ ላይ ተግባራዊ አለማድረጉ ፍፁም ትክክል ነው ሊባል የሚችል ነው፡፡ እንዲያውም በሥነ-ሥርዓት ደረጃ ሲታይም አስገዳጅነት የነበረው ተግባር ነው፡፡ ይህን አድርጎ ቢሆን ኖሮ፣ አጠቃላይ የሆነውን ሕግ ወደኋላ ተመልሶ አለመሥራት መርህን እና የአንቀጽ 65(1)ን የተለየ የሽግግር መመሪያ በጣሰ ነበር፡፡
ስለሆነም ችሎቱ የሕግ ክፍተቱን ለመሙላት የተከተለው አካሄድ መገምገም ያለበት ክሱ በቀረበበት ጊዜ (በ2013 ዓ.ም.) በነበረው የሕግ ማዕቀፍ ውስጥ ሆኖ ነው፡፡ በዚያን ወቅት፣ የከተማ መሬት ይዞታን ለማስመለስ የሚቀርብ ክስን በተመለከተ የተለየ የይርጋ ጊዜ ባለመኖሩ የተፈጠረውን የሕግ ክፍተት ለመሙላት በሕግ ሥርዓቱ ውስጥ የነበሩት አማራጮች፣ የፍትሐብሔር ሕጉ (በተለይም አንቀጽ 1677 እና 1845)፣ ወይም ደግሞ ቀድሞ የነበረው የገጠር መሬት አዋጅ (አዋጅ ቁጥር 456/1997) ብቻ ነበሩ (የኋለኛው አዋጅም ቢሆን በሰበር መ/ቁ 69302 እንደተረጋገጠው ለዚህ ክስ የሚሆን ግልጽ የይርጋ ጊዜ አላስቀመጠም ነበር)፡፡ ችሎቱ ክፍተቱን ለመሙላት የፍ/ህ/ቁ 1677(2) እና 1845ን (ጠቅላላ የ10 ዓመት ይርጋን) የመረጠ ሲሆን፣ ይህ ምርጫ የተደረገው በወቅቱ በነበረው የሕግ ሥርዓት ተጨባጭ ሁኔታ ላይ ተመሥርቶ ነው፡፡ የሕግ አውጪው ከጊዜ በኋላ ለገጠር መሬት ክሶች የተለየ እና የረዘመ የይርጋ ጊዜ ማውጣቱ የችሎቱን ውሳኔ ወደኋላ ተመልሶ ሕገ-ወጥ አያደርገውም፡፡ ይልቁንም፣ ፍርድ ቤቱ ገና ላልወጣ ሕግ እውቅና ሰጥቶ ወደኋላ ተግባራዊ አለማድረጉ የዳኝነት ሥልጣን ያለበትን የጊዜ ገደብ መረዳቱን እና የሕግ አውጪውንና የሕግ ተርጓሚውን የሥልጣን ክፍፍል ማክበሩን ያሳያል፡፡ በመሆኑም ባለሰባት ዳኞች ሰበር ችሎት የሕግን በጊዜ አተገባበር (Intertemporal law) መርህ የተገበረበት መንገድ ጉድለት የለሽ ነው፡፡ ችሎቱ አግባብነት ያለውን የጊዜ ማዕቀፍ በትክክል ለይቷል፤ ክሱ በቀረበበት ጊዜ የነበረውን ሕግ ተግብሯል፤ እንዲሁም ከዓመታት በኋላ የሚወጣን ሕግ አስቀድሞ ከመገመትና ከመተግበር ታቅቧል ለማለት ያስደፍራል፡፡
7.3 የአመሳስሎሽ ትርጓሜ ችግር፡ የሕግ ክፍተትን ለመሙላት በተመረጠው ምንጭ ላይ የታየ የፅንሰ-ሐሳብ (የዶክትሪን) መዛባት
ምንም እንኳን ችሎቱ የሕግን በጊዜ አተገባበር መርሆችን የተከተለበት መንገድ ተገቢነት ያለው ቢሆንም፣ የሕግ ክፍተቱን ለመሙላት የመረጠው የአመሳስሎሽ (Analogical) ድልድይ ግን ቀጣይነት ያለው አካዳሚያዊ ክርክር የሚሻ ከባድ የሕግ ፍልስፍና ጥያቄን ማስነሳቱ አይቀሬ መስሎ ታይቶኛል፡፡የዚህ ሂሳዊ ግምገማዬ መነሻም ችሎቱ የሕግ ክፍተቱን ለመሙላት (Gap-filling) ጥረት ማድረጉ አይደለም፤ ለከተማ መሬት ክስ የተለየ ይርጋ ባለመኖሩ ይህን ማድረጉ ተገቢና አስፈላጊ ነበር፣ ነገር ግን ትችቱ የሚያነጣጥረው በአመሳስሎሽ የወሰደውን የይርጋ ጊዜ ባመጣበት የተለየ ምንጭ ላይ በማተኮር ነው፡፡ ችሎቱ የከተማ መሬት ይዞታ ክርክርን የሚገዛ የይርጋ ጊዜ በሕግ አለመኖሩን ሲገነዘብ፣ ከፍትሐብሔር ሕጉ ሦስተኛ መጽሐፍ (ስለ ንብረት ሕግ) በመውጣት፣ ወደ አራተኛው መጽሐፍ (ስለ ግዴታዎች) ተሻገረ። በዚያም የውል ሕግ ደንቦች ከውል ውጭ በሆኑ ግዴታዎች ላይ ተፈፃሚ እንደሚሆኑ የሚደነግገውን አንቀጽ 1677(2) ድንጋጌን እንደ ማሻገሪያ ድልድይ በመጠቀም በፅሑፍ አቀማመጡ ውልን ለመፈፀም፣ ላለመፈፀም ወይም ለማፍረስ ለሚቀርቡ ክሶች የተዘጋጀውን በቁጥር 1845 ድንጋጌ ሥር የሚገኘውን አጠቃላይ የ10 ዓመት ይርጋ ተግባራዊ አድርጎታል። ይህ አካሄድ ከዚህ ቀደም ለገጠር መሬት ክርክሮች በሰበር መ/ቁ 69302 ከተወሰደው የትንታኔ መንገድ ጋር ሙሉ በሙሉ ተመሳሳይ ነው፡፡
ሆኖም የሕግ አውጪው በገጠር መሬት አስተዳደርና አጠቃቀም አዋጅ ቁጥር 1324/2016 የገጠር መሬትን ለማስመለስ የሚቀርብ ክስን የይርጋ ጊዜ በተመለከተ በራሱ ጊዜ ምላሽ ሲሰጥ፣ በአንቀጽ 64(2) ሥር ያስቀመጠው ገደብ 15 ዓመት እንጂ 10 ዓመት አልነበረም፡፡ ይህ የሕግ አውጪው ምርጫ በፅንሰ-ሐሳብ ደረጃ እጅግ ወሳኝ ነው፤ ምክንያቱም ለመሬት ማስለቀቅ ክሶች ተገቢ ነው ብሎ ያሰበው የጊዜ አድማስ ፍርድ ቤቱ በአመሳስሎሽ ከመረጠው የጊዜ ገደብ በእጅጉ የተለየ መሆኑን ያሳያልና፡፡ ከዚህም በላይ፣ የሕግ አውጪው የ15 ዓመትን ጊዜ መምረጡ የዘፈቀደ አልነበረም፡፡ ይህ ጊዜ በፍትሐብሔር ሕጉ አንቀጽ 1168 ሥር የማይንቀሳቀስ ንብረትን በተከታታይ ይዞታ እና ግብር በመክፈል (Adverse possession) ባለሀብት ለመሆን ከሚያስፈልገው የ15 ዓመት ጊዜ ጋር በትክክል ይገጠማል፡፡ ይህ መመሳሰል በግልጽ የሚያሳየው፣ የሕግ አውጪው የመሬት ማስለቀቅ ክስ ይርጋን ከንብረት ሕጉ የይዞታ መብት አሰጣጥ ጋር በማዛመድ (Calibrating) በንብረት መብት ማዕቀፍ ውስጥ ውስጣዊ ወጥነትን መፍጠሩን ነው፡፡
ይህ ምልከታ አንድ መሠረታዊ የስነ-ዘዴ (Methodological) ጥያቄን ቁልጭ አድርጎ ያጋልጣል፡፡ ይኸውም ችሎቱ የከተማ መሬት ማስለቀቅ ክስን (ወደ አንቀጽ 1168 የ15 ዓመት ይርጋ ከሚያመላክተው) የንብረት ሕግ አሠራር ይልቅ፣ (በአንቀጽ 1845 ወደ 10 ዓመት የሚያወርደው) የውል ግዴታ ጋር ማመሳሰል ለምን መረጠ? ጥያቄው አካዳሚያዊ ብቻ አይመስለኝም፡፡ በሲቪል ሎው የሕግ ሥነ-ዘዴ መሠረት፣ አንድ ፍርድ ቤት በአመሳስሎሽ ትርጓሜ የሕግ ክፍተትን ሲሞላ፣ አመሳስሎሹ መወሰድ ያለበት በጣም የጠበቀ የቅርብ ዝምድና ካለው የሕግ ማዕቀፍ (Nearest cognate legal regime)፣ ማለትም በውስጣዊ መርሆች፣ ዓላማዎች እና መዋቅር ከዋናው ጉዳይ ጋር እጅግ ከሚቀራረበው የሕግ
አካል ሊሆን እንደሚገባው ይታወቃል፡፡ የመሬት ይዞታ መብት (Holding rights)፣ የሰባት ዳኞች ችሎት ራሱ እንዳመነው፣ ተጨባጭ፣ የሚመዘገቡ፣ የሚተላለፉ እና መያዣ ሊሆኑ የሚችሉ፣ ከሁሉም ስዎች ልንጠይቃቸው የምንችላቸው (In rem) የንብረት መብቶች ናቸው፡፡ እነዚህ መብቶች ከግለሰቦች ጋር ብቻ ከሚያያዙ (Personal, inter partes) እና ፍጹም የተለየ መርህ ካላቸው የውል ግዴታዎች ጋር በመደባቸው አይገናኙም፡፡ አንድ ሕገ-ወጥ የመሬት ያዥ መሬቱን የመመለስ ግዴታ ያለበት፣ በነገር ላይ ያለን (In rem) መብት በመጣሱ እንጂ የውል ቃልን በማፍረሱ (Breach of contractual promise) አይደለም፡፡
ይህ የሕግ ባህሪ ታሳቢ ሲደረግ፣ ይበልጥ ፅንሰ-ሐሳባዊ ወጥነት (Doctrinal coherence) ያለው የአመሳስሎሽ ምንጭ ሊሆን የሚገባው የፍትሐብሔር ሕጉ የንብረት ድንጋጌዎች፤ በተለይም በአንቀጽ 1168 ሥር ያለው የ15 ዓመት ማዕቀፍ እንጂ የአራተኛው መጽሐፍ የውል ግዴታዎች ክፍል አልነበረም፡፡ የፍ/ህ/ቁ 1168 ድንጋጌ የማይንቀሳቀስ ንብረትን ለ15 ዓመት ከነግብሩ የያዘ ሰው የንብረቱ ባለቤት እንደሚሆን ይደነግጋል፡፡ ከዚህ በተቃራኒው በኩል ያለውን አመክንዮ ስናይ (ከመብቱ ለተነጠቀው ሰው አኳያ)፣ ንብረቱን በሕገ-ወጥ መንገድ የተነጠቀ ሰው መብቱን ለማስመለስ የሚችለውም በተመሳሳይ የ15 ዓመት ጊዜ ውስጥ መሆን አለበት የሚል መደምደሚያ ላይ ያደርሳል፡፡ ይህ ሚዛናዊ የሆነን ማዕቀፍ ይፈጥራል፡፡ በሌላ አገላለፅ ሕገ-ወጥ ያዡ መብት ለማግኘት 15 ዓመት ያስፈልገዋል፤ መብቱ የተነጠቀው ሰው ደግሞ መብቱን ለማስመለስ 15 ዓመት አለው ማለት ነው፡፡ በአንፃሩ ሰበር ችሎቱ የ10 ዓመቱን የውል ይርጋ መተግበሩ መዋቅራዊ አለመመጣጠንን (Asymmetry) የሚፈጥር ነው፡፡ ምክንያቱም ሕገ-ወጥ ያዡ ባለመብት ለመሆን አሁንም በአንቀጽ 1168 መሠረት 15 ዓመት ሲያስፈልገው፣ መብት የተነጠቀው ሰው ግን ከንብረት ሕጉ መዋቅር ጋር ምንም ዓይነት መዋቅራዊ ዝምድና በሌለው ሕግ መብቱን በ10 ዓመት ብቻ ያጣል የሚል መልዕክት አለው ማለት ነው፡፡
የሕግ አውጪው ከጊዜ በኋላ በአዋጅ ቁጥር 1324/2016 አንቀጽ 64(2) መሠረት ለገጠር መሬት ክስ የ15 ዓመት ይርጋ ማውጣቱ፣ ከላይ ለተነሳው ሂሳዊ ትንታኔ ከፍ ያለ ዋጋ ያለውን የማጠናከሪያ ድጋፍ የሚሰጥ ሁኖ ይገኛል፡፡ ምንም እንኳን ችሎቱ የሕግ አውጪውን ቀጣይ ውሳኔ አስቀድሞ ማወቅ ባይችልም፣ የሕግ አውጪው የወሰደው ምርጫ ግን ለመሬት ማስለቀቅ ክርክሮች ትክክለኛው የፅንሰ-ሐሳብ (የዶክትሪን) መሠረት የፍ/ህ/ቁጥር 1168 ድንጋጌ የንብረት ሕግ አመክዮ እንጂ የቁጥር 1845 ድንጋጌ የውል ሎጂክ አለመሆኑን ያረጋግጣል፡፡ የሕግ አውጪው የይርጋ ሥርዓቱን ከውል ይልቅ ከንብረት ሕግ ማዕቀፍ ጋር ማጣመሩ የሚያሳየው፣ የችሎቱ የአመሳስሎሽ ድልድይ በፅሑፋዊ ትርጓሜ ሊደገፍ የሚችል ቢሆንም በፅንሰ-ሐሳብ (በዶክትሪን) ደረጃ ግን አጥጋቢ አለመሆኑን (Doctrinally suboptimal) ነው፡፡
በመሆኑም አዲሱ አስገዳጅ የሰበር ውሳኔ (ለከተማ መሬት ክስ የ10 ዓመት ይርጋን ማስቀመጡ) እና ከእርሱ በፊት የወጣው አዋጅ ቁጥር 1324/2016 (በአንቀጽ 64(2) ለገጠር መሬት ክስ የ15 ዓመት ይርጋን መደንገጉ) መገጣጠም፣ በኢትዮጵያ የመሬት ሕግና የአስገዳጅ የህግ ትርጉም ላይ ያልታሰበ እና ከፍተኛ አንድምታ ያለው የይርጋ ጊዜ መከፈል (Bifurcation of limitation periods) ይዞ ተከስቷል፡፡ ከዚህ አንፃር አሁን በተጨባጭ ባለው ነባራዊ የሕግ ማዕቀፍ መሠረት፡-የይዞታ መብቱ በሕገ-ወጥ ያዥ የተጣሰበት የገጠር መሬት ባለይዞታ፣ መብቱን ለማስመለስ የሚያስችል የ15 ዓመት ጊዜ አለው (በአዋጅ 1324/2016 አንቀጽ 64(2) መሠረት) ሲኖረው ፍጹም ተመሳሳይ በሆነ ሁኔታ ውስጥ የሚገኝ የከተማ መሬት ባለይዞታ ግን በአዲሱ የሰበር ውሳኔ እና በፍ/ብ/ሕ/ቁ 1677(2) እና 1845 ደንጋጌዎች መሠረት የ10 ዓመት ጊዜ ብቻ ይኖረዋል ማለት ነው፡፡
ይህን ልዩነት በጠንካራ መርህ ላይ ተመሥርቶ ለማስረዳትና አሳማኝ ለማድረግ እጅግ አዳጋች ነው፡፡ ምክንያቱም የገጠርም ሆነ የከተማ መሬት ይዞታ መብቶች የሚመነጩት ከአንድ ዓይነት ሕገ-መንግሥታዊ መሠረት፤ ማለትም መሬት (የገጠርም ሆነ የከተማ) የመንግስትና የሕዝብ ንብረት መሆኑን ከሚያውጀውና የግል ባለቤትነትን ከሚከለክለው የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ሕገ-መንግሥት አንቀጽ 40(3) ነውና፡፡ የመብቱ ባህሪ (ከባለቤትነት ያነሰ ነገር ግን በነገር ላይ ያለ ከሁሉም ሰዎች ልንጠይቀው የምንችለው (In rem) ተጨባጭ የንብረት መብት መሆኑ) መሬቱ የሚገኘው በከተማ ክልል ውስጥ ሆነም በገጠር፣ በተጠቃሹ ሕገ-መንግሥታዊ ድንጋጌ ዕይታ አንድ ዓይነት ነው፡፡
የሕገ-መንግሥታዊ መሠረቱ አንድ ዓይነት ከሆነ፣ ለባለይዞታዎች የሚሰጠው የሕግ ከለላም በመርህ ደረጃ አንድ ዓይነት ሊሆን ይገባል፡፡ ለገጠር መሬት ባለይዞታ 15 ዓመት እየተሰጠ የከተማውን ባለይዞታ በ10 ዓመት መገደብ ምክንያታዊ የሆነ የፖሊሲ መሠረት (Rational policy basis) የሌለው ልዩነትን መፍጠር ሲሆን፣ ይህ ደግሞ ሰባት ዳኞች የተሰየሙበት ችሎት የተቃረኑ ውሳኔዎችን በማረም ሊያመጣው የፈለገውን የሕግ ወጥነት (Doctrinal consistency) የሚሸረሽር ነው፡፡
አንድ ሰው የከተማ እና የገጠር መሬት የተለያዩ ማሕበራዊና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳዎች እንዳላቸው፣ በተለያዩ የቁጥጥር ሥርዓቶች እንደሚመሩ፣ እና የክርክሮቹም ተጨባጭ ሁኔታዎች እንደሚለያዩ በማንሳት፣ ይህ ልዩነት የተለያየ የይርጋ ጊዜን ተገባራዊ ማድረግ እንደሚችል ይሞግት ይሆን ይሆናል፡፡ ይሁን እንጂ እንዲህ ዓይነቱ መከራከሪያ፣ የከተማ መሬት የይዞታ ሥርዓት ከገጠሩ ይበልጥ መደበኛ፣ በሰነድ የተደገፈ፣ እና በአስተዳደር ሥርዓት የተደራጀ ነው የሚለውን መደበኛ አስተሳሰብ ወደ ጎን ትቶ፣ የከተማ ባለይዞታ መብቱን ለመጠየቅ ከገጠሩ ባለይዞታ ያነሰ ጊዜ ሊሰጠው የሚገባው ለምንድን ነው? የሚለውን አሳማኝ በሆነ መንገድ ማስረዳት ይጠበቅበታል፡፡ እንዲያውም፣ በገጠር መሬት ይዞታ ላይ ያለው ሰፊ ኢ-መደበኛነት እና የሰነድ አያያዝ ክፍተት፣ መረጃዎች በገጠሩ አካባቢ ቶሎ ስለሚጠፉ፣ ለገጠር መሬት ክስ ከከተማው ያጠረ (ያልረዘመ) የይርጋ ጊዜ ሊያስፈልግ ይችላል ወደሚል ንድፈ-ሐሳባዊ መከራከሪያ ሊያመራን ይችላል፡፡ አሁን በህጉና በአስገዳጅ የህግ ትርጉም የተወለደው ዥንጉርጉር ሥርዓት ማለትም ገጠር 15 ዓመት፣ የከተማ 10 ዓመት ይርጋ ጊዜ እንዲሆን የተደረገበት ኩነት ይህንን ሎጂክ/አመክንዮ/ የተገላቢጦሽ ያደርገዋል፡፡
7.4 የክፍል 7 ጥማቂ
የሰባት ዳኞች ችሎት በዚህ ጉዳይ ላይ የሕግን በጊዜ አተገባበር (Intertemporal law) ያስተናገደበት መንገድ እንከን የለሽ (Flawless) ነው ሊባል የሚችል ቢሆንም ችሎቱ ክሱ በቀረበበት ጊዜ (በ2013 ዓ.ም.) የነበረውን የሕግ ማዕቀፍ በመተግበር፣ የሕግ ክፍተቱን በወቅቱ በነበሩ የፍትሐብሔር ሕግ ድንጋጌዎች በመሙላት፣ እና ገና ፀድቆ ላልወጣ አዋጅ (አዋጅ ቁጥር 1324/2016) ወደኋላ ተመልሶ የሚሠራ የተፈፃሚነት ኃይል ላለመስጠት መወሰኑ በሥነ-ሥርዓትም ሆነ በመሰረታዊ ህግ ይዘት ችግር የለውም፡፡ በወቅቱ ላልነበረ ሕግ አልተገበርክም ተብሎ ችሎቱን መተቸት የሚቻልበት የህግ አግባብ የለም፡፡ እንዲሁም የአዋጅ ቁጥር 1324/2016 የአንቀጽ 65(1)
የሽግግር ድንጋጌ ራሱ አዲሱ ሕግ በመታየት ላይ ባሉ ጉዳዮች ላይ እንደማይሠራ በማረጋገጥ ይህንን ያጠናክረዋል፡፡ ሆኖም ችሎቱ የሕግ ክፍተቱን ለመሙላት የመረጠው የአመሳስሎሽ ድልድይ፤ ማለትም ከአራተኛው መጽሐፍ (የግዴታዎች ሕግ) የተወሰደው የፍ/ብ/ሕ/ቁ 1845 የ10 ዓመት ይርጋ፣ የሕግ አውጪው ከጊዜ በኋላ በአዋጅ 1324/2016 አንቀጽ 64(2) ለገጠር መሬት ክስ የ15 ዓመት ይርጋን መደንገጉን ስናይ በፅንሰ-ሐሳብ (በዶክትሪን) ደረጃ የጎላ ክፍተት ያለበት ሆኖ ይታያል፡፡ የሕግ አውጪው የገጠር መሬት ይርጋን የ15 ዓመት የይዞታ (Adverse possession) ሥርዓት ከሚደነግገው የፍ/ብ/ሕ/ቁ 1168 ጋር ማጣመሩ፣ ለመሬት ማስለቀቅ ክሶች ተፈጥሯዊ እና ፅንሰ-ሐሳባዊ ወጥነት ያለው የአመሳስሎሽ ምንጭ የሚገኘው በንብረት ሕጉ ማዕቀፍ ውስጥ እንጂ በውል ግዴታዎች ማዕቀፍ ውስጥ አለመሆኑን የሚያስገነዝብ ሁኖ ይገኛል ችሎቱ ከፍ/ህ/ቁጥር 1168 ይልቅ አንቀጽ 1845 ድንጋጌን መምረጡ በፅሑፋዊ ትርጓሜ ሊደገፍ የሚችል ቢሆንም፣ በኢትዮጵያ የመሬት ሕግ ውስጥ ሁለት የተምታታ እና የሚጋጭ ሥርዓት (Dual and conflicting regime) ይዞ ብቅ ብሏል፡፡ ምንም እንኳን ሕገ-መንግሥታዊ መሠረታቸው እና የመብታቸው የሕግ ባህሪ አንድ ዓይነት ቢሆንም፣ የከተማ መሬት ክስ በ10 ዓመት፣ የገጠር መሬት ክስ ደግሞ በ15 ዓመት እንዲታገድ ማድረግ የህግ ባለሙያውንም ሆነ ሌላውን የማህበረሰብ ክፍል የሚያሳምን ሊሆን አይችልም፡፡
ይህ ሥርዓታዊ አለመጣጣም ከሁለት በአንዱ መንገድ ዕልባት እስካላገኘ ድረስ የኢትዮጵያን የንብረት ሕግ ስነ ህግ እድገና የአስገዳጅ ህግ ትርጉም ወጥነት ግብ በፅኑ መፈተኑን የሚይቀጥል መሆኑ ይገመታል፡፡ ስለሆነም ባለሰባት ዳኞች ሰበር ችሎት ለከተማ መሬት የሰጠውን አስገዳጅ ትርጉም ከፍ/ህ/ቁጥር 1168 መሰረተ ሃሳብና ከተገቢው የህግ አተረጓጎም ስልት አንፃር በድጋሚ በመገምገም በቅርብ ጊዜ በወጣው የገጠር መሬት ህግ ውስጥ ከተደነገገው የ15 ዓመት ማዕቀፍ ጋር ያጣጥመዋል፣ አለበለዚያ ደግሞ የሕግ አውጪው (ፓርላማው) ከገጠር መሬት ሥርዓት ጋር የተናበበ የይርጋ ድንጋጌን ያካተተ አጠቃላይ የከተማ መሬት አስተዳደር አዋጅ ያወጣል፡፡ ከፍ ሲል ደግሞ የፌዴሬሽን ምክር ቤት ከላይ ከተጠቀሰው ህገ መንግስቱ ጥበቃ አንፃር አይቶ ህገ መንግስታዊ ትርጉም ሊሰጠበት ይችላል፡፡ ይህ የእርምት እርምጃ እስኪወሰድ ድረስ ለአንድ ዓይነት ሕገ-መንግሥታዊ መብት፤ በከተማ 10 ዓመት፣ በገጠር 15 ዓመት ሊሆን ይገባል ተብሎ የተከፋፈለው የይርጋ ጊዜ በኢትዮጵያ የመሬት ሕግ እና በአስገዳጅ የህግ ትርጉም ስርዓት ላይ ያልተፈታ ፅንሰ-ሐሳባዊ መዛባት (Doctrinal anomaly) ሆኖ መቀጠሉ አይቀሬ ነው፡፡ በመሆኑም ይህ በችሎቱ ውሳኔ እንደድክመት ሊነሳ የሚችል ተገቢ ምልክታ ነው የሚል እምነት አለኝ፡፡
ክፍል ስምንት፡ አጠቃላይ ማጠቃለያ
የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የሰባት ዳኞች ሰበር ችሎት የሰጠው ይህ ውሳኔ ተቃርኖ ያለባቸውን አስገዳጅ የህግ ትርጉሞችን ከማረቅና የስርዓቱን ወጥነትና ተገማችነት ከማስፈን አንፃ እጅግ መሠረታዊ እና አስፈላጊ ቢሆንም በአገሪቱ የንብረት እና የመሬት ሕግ ስነ ህግ ላይ ህገ መንግስታዊ መሰረትን ባልተጎናፀፈ አመክንዮ ተመሳሳይ ጥበቃ ያለውን የባለይዞታነት መብት በተለያዩ የይርጋ ጊዜያት እንዲገዙ ስርዓት ያበጀ በመሆኑ አከራካሪነቱ አይቀሬ ይመስለኛል፡፡ ውሳኔው በቀድሞ አስገዳጅ ውሳኔዎች መካከል የነበረውን ጥልቅ ተቃርኖ ሕገ-መንግሥታዊ መሠረትን እና የፍትሐብሔር ሕግን አግባብነት ያላቸውን መርሆች በሚገባ በመመርመር ተገቢውን የዳኝነት ጥበብ በመጠቀም ለመፈታት የተቻለበት መሆኑ ይታመናል፡፡ በተለይም የባለቤትነት መብትን (Ownership) ከይዞታ መብት (Holding rights) በሚገባ በመለየት፣ ለባለቤትነት የተፈጠሩ የሕግ ማዕቀፎችን የግል የመሬት ባለቤትነት በማይፈቅድ ሕገ-መንግሥታዊ ሥርዓት ውስጥ በቀጥታ ተግባራዊ ማድረግ የማይቻል መሆኑን አሳይቷል፡፡ ይህ የሕግ ትርጉም በኢትዮጵያ የከተማ መሬት ይዞታ ክርክሮች ላይ ፅንሰ-ሐሳባዊ ጥራትን፣ ሥርዓታዊ ወጥነትን እና ተገማችነትን በማምጣት ወደፊት ለሚነሱ የንብረት ሕግ ክርክሮች ጠንካራ መሠረት የሚጥል አንፀባራቂ የዳኝነት አሻራ ነው ተብሎ ቢውሰድ ማጋነን አይሆንብኝም፡፡ ሆኖም ከላይ በክፍል 7 ስር በሰፊው እንደተብራራው ችሎቱ የሕግ ክፍተቱን ለመሙላት የመረጠው የአመሳስሎሽ ድልድይ፤ ማለትም ከአራተኛው መጽሐፍ (የግዴታዎች ሕግ) የተወሰደው የፍ/ብ/ሕ/ቁ 1845 የ10 ዓመት ይርጋ፣ የሕግ አውጪው ከጊዜ በኋላ በአዋጅ 1324/2016 አንቀጽ 64(2) ለገጠር መሬት ክስ የ15 ዓመት ይርጋን መደንገጉን ስናይ በፅንሰ-ሐሳብ (በዶክትሪን) ደረጃ የጎላ ክፍተት ያለበት ሆኖ ይታያል፡፡ ስለሆነም ችሎቱ በራሱ አነሳሽነት የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ወይስ የፌዴፌሬሽን ምክር ቤት? ትክክለኛውን መስመስር ይለዩ ይሆን? በዚህ ነጥብ ላይ ሁላችንንም ሊያስተምር የሚችል የምርምር ስራ ወይም የውሳኔ ትችት እይታ በዘርፉ በበቁ በአወቁ የአገራችን ምሁራን ሊከናወን እንደሚችል ተስፋ አደርጋለሁ፡፡
አበቃ!!
ተፃፈ በአልማው ወሌ
መጋቢት 04 ቀን 2018 ዓ/ም
አዲስ አበባ
ማስታወሻ፦ ፅሁፉ ጥብቅ የምርምር ዘዴ በመከተል ያልተከናወነ መሆኑን ከወዲሁ እየገለፅሁ ለወደፊቱ ግን በዚሁ አርዕስትና ተያያዥ የህግ ጉዳዮች ላይ ፈጣሪ አምላክ ፍቃዱ ከሆነ ሙያዊ እና አካዳሚያዊ ደረጃውን የጠበቀ ስራ ይዠ ለመቅረብ እሞክራለሁ፡፡ ማናቸውም ስህተቶች የራሴው መሆናቸው እንዲታወቅልኝም እፈልጋለሁ፡፡
https://www.facebook.com/s...
https://www.facebook.com/s...
(የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በሰባት ዳኞች በተሰጠ የህግ ትርጉም የተሰጠ የህግ ትንታኔ)
#ethiopia | በጠበቃና የህግ አማካሪ አልማው ወሌ የኢትዮጵያ ፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ከሰባት ያላነሱ ዳኞች የተሰየሙበት የሰበር ችሎት የካቲት 30 ቀን 2018 ዓ.ም በመ.ቁጥር 244308 የከተማ መሬት ይዞታን ለማስመለስ የሚቀርብ ክስ በይርጋ ይታገዳል ወይስ አይታገድም ? በሚለው አከራካሪ የህግ ነጥብ ላይ ሰበር ችሎቱ በሰጠው አስገዳጅ የሕግ ትርጉም ላይ የቀረበ አጭር ትንታኔ
የተከበሩ ጠበቃ እናመሠግናለን መልካም ንባብ
ኢትዮጵያ ፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ከሰባት ያላነሱ ዳኞች የተሰየሙበት የሰበር ችሎት የካቲት 30 ቀን 2018 ዓ.ም በመ.ቁጥር 244308 ላይ በሰጠው አስገዳጅ የሕግ ትርጉም ላይ የቀረበ አጭር ትንታኔ 1
ክፍል አንድ፡ መግቢያ እና የሥነ-ሥርዓት ዳራ 1
ክፍል ሁለት፡ የሦስቱ ቀደምት አስገዳጅ ውሳኔዎች አጠቃላይ ትንታኔ 1
ክፍል አራት፡ የሰባት ዳኞች ችሎት አዲሱ የሕግ ትርጉም 3
ክፍል አምስት፡ ተግባራዊ የተደረጉት የፍትሐብሔር ሕግ ድንጋጌዎች ትንታኔ 4
ክፍል ስድስት፡ ስለ አዲሱ ትርጉም ጥንካሬዎች 4
ክፍል ሰባት፡ የውሳኔው ማጠቃለያ እና ቀጣይ አንድምታዎች 4
7.1 አዲሱን ሕግ በመታየት ላይ ባሉ ጉዳዮች ላይ ያለመተግበር ትክክለኛነት፡ የሽግግር ድንጋጌዎችን በጥብቅ መከተል 5
7.2 የአመሳስሎሽ ትርጓሜ ችግር፡ የሕግ ክፍተትን ለመሙላት በተመረጠው ምንጭ ላይ የታየ የፅንሰ-ሐሳብ (የዶክትሪን) መዛባት 6
7.3 የክፍል 7 ጥማቂ 8
ክፍል ስምንት፡ አጠቃላይ ግምገማ 9
የኢትዮጵያ ፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ከሰባት ያላነሱ ዳኞች የተሰየሙበት የሰበር ችሎት የካቲት 30 ቀን 2018 ዓ.ም በመ.ቁጥር 244308 ላይ በሰጠው አስገዳጅ የሕግ ትርጉም ላይ የቀረበ አጭር ትንታኔ
ክፍል አንድ፡ መግቢያ እና የሥነ-ሥርዓት ዳራ
ከሰባት ያላነሱ ዳኞች የተሰየሙበት የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት የካቲት 30 ቀን 2018 ዓ.ም. የሰጠው ይህ ውሳኔ በመ/ቁጥር 210477 ላይ ተሰጥቶ የነበረውን አስገዳጅ የህግ ትርጉም በመለወጥ ተሰጠው (Overruling) ውሳኔ ሲሆን በአገሪቱ የንብረት ሕግ ስነ ህግ እድገት እና በአስገዳጅ የህግ ትርጉም ስርዓት ላይ የራሱ የሆነ አንድምታ ያለው መሆኑ ይታመናል፡፡ ይህ አዲስ አስገዳጅ የህግ ትርጉም ለውጥ በችሎቱ የተሰጠው በፌዴራል ፍርድ ቤቶች አዋጅ ቁጥር 1234/2013 አንቀጽ 26(1) ድንጋጌ እና በሰበር ስነ ስርዓት መመሪያ ቁጥር 17/2015 አንቀፅ 14(2) በተዘረጋው ስርዓት ሲሆን ችሎቱ የተሰየመበትም ዋነኛ ምክንያትም የከተማ መሬት ይዞታን ለማስመለስ የሚቀርብ ክስ በይርጋ ይታገዳል ወይስ አይታገድም ? በሚለው አከራካሪ የህግ ነጥብ ላይ ሰበር ችሎቱ ቀደም ሲል በሰጣቸው አስገዳጅ ውሳኔዎች መካከል ሊታረቅ የማይችል ተቃርኖ በመፈጠሩ ነው፡፡ የጉዳዩ ምንጭ አቶ ጅላሎ ኩመል ሼህረዲ (አመልካች/ተከሳሽ) እና አቶ ታምራት መርከቡ ፍልቾ (ተጠሪ/ከሳሽ) በአዲስ አበባ ከተማ (ለሚ ኩራ ክፍለ-ከተማ፣ ወረዳ 08፣ ፊጋ ሰፈር በሚባል አካባቢ) በሚገኝ 2,000 ካሬ ሜትር የከተማ ቦታ ላይ ያደረጉት ክርክር ነው፡፡ ጉዳዩ ለሰባት ዳኞች ችሎት መመራቱ ሥነ-ሥርዓታዊ ሂደት ብቻ ሳይሆን ጥልቅ መሠረታዊ የሕግ ይዘት ያለው ጉዳይ ሲሆን ችሎቱም በሕግ አተገባበር ላይ ወጥነት እና ተገማችነትን የማረጋገጥ ኃላፊነቱን ለመውጣት በተጠቃሽ ውሳኔዎቹ መካከል የታየውን ተቃርኖ አስታራቂ እና ግልጽ አቋም ሊያዝበት የሚገባ መሆኑን በግልጽ አስፍሯል፡፡ ይህ እርስ በእርሱ የሚቃረኑ አስገዳጅ ውሳኔዎች ሥርዓታዊ የሆነ ችግር እንዳያስከትሉ ችሎቱ ራሱን በራሱ በማረም የወሰደው ዕርምጃ በኢትዮጵያ የአስገዳጅ የህግ ትርጉም ሥርዓት ውስጥ ያለውን ተቋማዊ ብስለት የሚያሳይ ነው ተብሎ ሊወሰድ የሚገባው ነው፡፡
ክፍል ሁለት፡ የሦስቱ ቀደምት አስገዳጅ ውሳኔዎች አጠቃላይ ትንታኔ
በመጀመሪያ ደረጃ በሰበር መዝገብ ቁጥር 43600 ጥር 05 ቀን 2002 ዓ.ም. የተወሰነውንና በቅጽ 10 የታተመውን አስገዳጅ የህግ ትርጉም በአጭሩ ስንመለከት ጉዳዩ አቶ ዳዊት መስፍን ከተጠሪ የመንግስት ቤቶች ኤጀንሲ ጋር ያደረጉት ክርክር ነበር፡፡ አቶ ዳዊት በአዲስ አበባ ከተማ (የቀድሞ ወረዳ 118፣ ቀበሌ 05) የሚገኝ መኖሪያ ቤት የባለቤትነት መብትን መሠረት በማድረግ ቤቱ እንዲለቀቅላቸው ክስ አቅርበው ነበር፡፡ ለዚህም በጥቅምት 23 ቀን 1985 ዓ.ም. የተሰጠ የከተማ ቤት ባለቤትነት ማረጋገጫ ደብተር አቅርበዋል፡፡ ተጠሪው (ኤጀንሲው) በበኩሉ፣ የፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 1845ን ማለትም የ10 ዓመቱን የውል ግዴታዎች ይርጋ ድንጋጌ በመጥቀስ የይርጋ መቃወሚያ አቅርቦ ነበር፡፡ የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት እና የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የይርጋ መቃወሚያውን በመቀበል ክሱን ውድቅ አድርገውት ነበር፡፡ ጉዳዩ የቀረበለት የሰበር ችሎት ግን የማይንቀሳቀስ ንብረትን በተመለከተ የሚቀርብ የመፋለም ክስ በይርጋ ቀሪ የሚሆንበት አግባብ መኖር አለመኖሩን ጭብጥ አድርጎ በመያዝ ጥልቅ ትንታኔ ሰጥቷል፡፡ የሰበር ችሎቱ ትንታኔውን የጀመረው ማናቸውም ኢትዮጵያዊ የንብረት ባለቤት መሆኑ በሕገ-መንግስቱ አንቀጽ 40(1) የተረጋገጠ መሆኑን በማንሳት ሲሆን፣ በመቀጠልም የፍትሐብሔር ሕጉን የንብረት ድንጋጌዎች ማለትም አንቀጽ 1126፣ 1168፣ 1184፣ እና 1186 ደንጋጌዎችን እንዲሁም በፍ/ህ/ቁጥር 1188 እስከ 1192 ድረስ ያሉትን ድንጋጌዎችን ሙሉ ይዘትና መንፈስ በዝርዝር ተመልክቷል፡፡ ችሎቱ ወሳኝ ብሎ ያነሳው ነጥብ የፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 1192 "ባለሀብትነትን የሚያስቀር የይርጋ ዘመን" ብሎ ያስቀመጠው ለሚንቀሳቀስ ንብረት ብቻ መሆኑን እና ስለ ማይንቀሳቀስ ንብረት በዝምታ ማለፉን ነው፡፡ ከዚህም በተጨማሪ በአንቀጽ 1206 ሥር የተደነገገው የመፋለም ክስ የባለቤትነት መብት ከሁሉ የሰፋ መብት መገለጫ መሆኑን፣ እና የማይንቀሳቀስ ንብረት ባለቤትነት ዘላቂነት (Perpetuity) ያለው መብት በመሆኑ በይርጋ ቀሪ እንዳይሆን የሕግ አውጪው ፍላጎት መሆኑን አብራርቷል፡፡ በዚህም መሠረት የፍ/ብ/ሕ/ቁ 1845 ድንጋጌን ተፈፃሚ ማድረግ የሕጉን አወቃቀርና መንፈስ የሚያፋልስ መሆኑን በመግለጽ፣ የማይንቀሳቀስ ንብረት የመፋለም መብት ክስ በይርጋ ቀሪ አይሆንም ወደሚል ድምዳሜ ደርሷል፡፡ ይህ ውሳኔ በፅንሰ-ሐሳብ ደረጃ ጠንካራ ቢሆንም፣ ዋነኛ ክፍተቱ ትንታኔው ሙሉ በሙሉ ታሳቢ ያደረገው "የግል ባለቤትነት መብት" (Private Ownership) መኖርን መሆኑ ነው፡፡ ጉዳዩ መኖሪያ ቤትን የሚመለከት ስለነበር ይህ አካሄድ ትክክል ቢሆንም፣ የባለቤትነት መብት በሕገ-መንግሥት በተከለከለበት መሬት ላይ ትንታኔው እንዴት ሊተገበር ይችላል ለሚለው ጥያቄ ምላሽ የሚሰጥ አልነበረም፡፡ ሆኖም ትርጉም በሌሎች ልዩ ህጎች ያሉትን የይርጋ ድንጋጌዎችን የማይነካ መሆኑ በማሳሳብ አልፏል፡፡
በሁለተኛ ደረጃ በሰ/መ/ቁጥ 69302 ታህሳስ 20 ቀን 2004 ዓ.ም. የተሰጠውን አስገዳጅ የህግ ትርጉም ስንመለከት፦ ጉዳዩ በአመልካች አቶ ሸለማ ነገሰ እና በተጠሪ አቶ ፋይሣ መንግስቱ መካከል በኦሮሚያ ክልል፣ ኖኖ ቤንጃ ወረዳ በሚገኝ የገጠር እርሻ መሬት ላይ የተደረገ ክርክር ነው፡፡ ተጠሪ አባቴ በሞት ከተለየበትמ 1985 ዓ.ም.
ጀምሮ አመልካች መሬቱን አላግባብ ስለያዘብኝ ይልቀቅልኝ ሲል ክስ ያቀረበ ሲሆን አመልካች በበኩሉ መሬቱን ለ18 ዓመታት መያዙን በመግለጽ ተከራክሯል፡፡ የስር ፍርድ ቤቶች መሬቱ እንዲለቀቅ የወሰኑ ቢሆንም የሰበር ችሎቱ ግን አርሶ አደሮች የእርሻ መሬት የማግኘትና ያለመፈናቀል መብት እንዳላቸው ሕገ-መንግሥቱ በአንቀጽ 40(4) መሠረት ማረጋገጡን ጠቅሶ፣ ይሁን እንጂ መሬቱን በሌላ ሰው የተነጠቀ አርሶ አደር ክስ ማቅረብ ስላለበት የጊዜ ገደብ የገጠር መሬት አዋጆች በግልጽ አለመደንገጋቸውን በማንሳት የሕግ ክፍተት መኖሩን አሳይቷል፡፡ የፍትሐብሔር ሕጉ የሁከት ይወገድልኝ ክስ የ2 ዓመት ይርጋን (አንቀጽ 1149(2)) መተግበር የአርሶ አደሩን ሕገ-መንግሥታዊ መብት አጥብቦ የሚገድብ በመሆኑ ውድቅ በማድረግ፣ በፍ/ብ/ሕ/ቁ 1677(1) ስር የተመለከተውን ድንጋጌ እንደ ድልድይ በዋቢነት በመጥቀስ የፍ/ብ/ሕ/ቁ 1845 የ10 ዓመት ይርጋ በገጠር መሬት ይዞታ ላይ ተግባራዊ እንዲሆን ወስኗል፡፡ ይህ ውሳኔ ምንም እንኳን ከመዝገብ ቁጥር 43600 ፈጽሞ የተለየ አቀራረብ ይዞ የመሬት ይዞታን ከባለቤትነት መብት ነጥሎ በማየት የ10 ዓመት ይርጋ ተግባራዊ ያደረገ ቢሆንም፣ የውል ድንጋጌ የሆነውን የፍ/ህ/ቁ 1845 ድንጋጌን በቀጥታ መሬት ላይ ለመተግበር የሄደበት መንገድ በበቂ ሁኔታ ያልተብራራ መሆኑ እንደ ሂሳዊ ድክመት ሊነሳበት ይችላል፡፡
በሦስተኛ ደረጃ በሰ/መ/ቁ 210477 ታህሳስ 27 ቀን 2014 ዓ.ም. የተወሰነውንና አሁን የተሻረውን ስንመለከት፣ ጉዳዩ በአዲስ አበባ ከተማ ቦሌ ክፍለ-ከተማ ውስጥ የሚገኝ የከተማ መሬት ይዞታን በተመለከተ በአመልካቾች (የአቶ ነጋሳ ዱቤ ወራሾች) እና በተጠሪዎች (ወ/ሮ ጸሐይ ቹቾ እና ወ/ሮ ሴደሬ ንጉሴ) መካከል የተደረገ ክርክር ነበር፡፡ ተጠሪዎች ቦታውን ከ1993 ዓ.ም. ጀምሮ ለ19 ዓመታት መያዛቸውን በመግለጽ የይርጋ መቃወሚያ አቅርበው የስር ፍርድ ቤቶችም መቃወሚያውን ተቀብለውት ነበር፡፡ ሆኖም የሰበር ችሎቱ ይህንን ውሳኔ በመሻር፣ የቀረበው ክስ "የመፋለም ክስ" መሆኑን በመግለጽ የቤትን ባለቤትነት የተመለከተውን የሰ/መ/ቁ 43600 አመክንዮ በቀጥታ በመዋስ "የከተማ መሬት ይዞታን በተመለከተ የሚቀርብ የመፋለም ክስ በይርጋ አይታገድም" የሚል አስገዳጅ ትርጉም ሰጥቶ ነበር፡፡ የዚህ ውሳኔ ዋነኛ ስህተት የባለቤትነት መብትን (Ownership) እና የይዞታ መብትን (Holding rights) አንድ አድርጎ ማየት መቻሉ ነው፡፡ ሕገ-መንግሥቱ በአንቀጽ 40(3) መሠረት ግለሰቦች በመሬት ላይ የባለቤትነት መብት እንደሌላቸው እየደነገገ፣ በሰ/መ/ቁ 210477 የተሰጠው አስገዳጅ የህግ ትርጉም ግን የባለቤትነት መብት ጥበቃን (ከይርጋ ነፃ መሆንን) በመሬት ይዞታ መብት ላይ በመተግበሩ መሠረታዊ የሆነ የፅንሰ-ሐሳብ እና የሕግ ስህተት ተፈጽሞበት የነበረ ጉዳይ ነው፡፡
ክፍል ሦስት፡ በውሳኔዎቹ መካከል የነበረው ተቃርኖ እና የሕግ ማዕቀፎች
በእነዚህ ሦስት ውሳኔዎች መካከል የተፈጠረው ተቃርኖ እጅግ የጎላ እንደነበር በቀላሉ መገንዘብ ይቻላል፡፡ በአንድ በኩል መዝገብ ቁጥር 43600 በቤት ባለቤትነት ላይ የመፋለም ክስ ይርጋ የለውም ሲል፣ በሌላ በኩል በሰ/መ/ቁ 69302 በገጠር መሬት ይዞታ ላይ የ10 ዓመት ይርጋ ተፈፃሚ አድርጓል፡፡ በተቃራኒው ደግሞ በሰ/መ/ቁ 210477 የከተማ መሬት ይዞታን አስመልክቶ የቀረበን ክርክር የባለቤትነት ጉዳይ ከሆነው ከሰ/መ/ቁ 43600 ጋር በማመሳሰል የከተማ መሬት ክስ በይርጋ አይታገድም በማለት ወስኗል፡፡ ይህ ሁኔታ በመሬት ይዞታዎች (በገጠር እና በከተማ) ላይ የተለያየ እና ምክንያታዊ ያልሆነ የይርጋ አተገባበር እንዲፈጠር አድርጎ የነበረ መሆኑ ከውሳኔዎቹ በግልፅ ይታያል፡፡
ይህንን ተቃርኖ ለመፍታት የሰባት ዳኞች ችሎት በርካታ ሕጎችን አንድ ላይ መመርመር ነበረበት፡፡ ከእነዚህም ውስጥ የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ሕገ-መንግሥት አንቀጽ 40(3) ስለ መሬት የመንግስትና የሕዝብ ንብረትነት፣ አንቀጽ 40(4) ስለ አርሶ አደሮች መብት፣ እና አንቀጽ 40(7) በጉልበትና በገንዘብ ስለሚፈራ ንብረት ያካተቱት ድንጋጌዎች ይገኙበታል፡፡ በተጨማሪም የፍትሐብሔር ሕግ አንቀጽ 1192፣ አንቀጽ 1206 (ስለ መፋለም ክስ)፣ አንቀጽ 1149(2) (የሁከት ክስ ይርጋ)፣ እንዲሁም አንቀጽ 1677(2) እና 1845 ድንጋጌዎች ሙሉ ይዘታቸው ተፈትሸዋል፡፡ ከእነዚህ በተጨማሪም የከተማ ቦታ በሊዝ ስለመያዝ የወጣው አዋጅ ቁጥር 721/2004፣ የከተማ መሬት ይዞታ ምዝገባ አዋጅ ቁጥር 818/2006 እና የገጠር መሬት አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 1324/2016 አግባብነት ያላቸው የሕግ ማዕቀፎች በመሆናቸው በችሎቱ ታሳቢ ተደርገዋል፡፡
ክፍል አራት፡ የሰባት ዳኞች ችሎት አዲሱ የሕግ ትርጉም
ሰባት ዳኞች የተሰየሙበት የሰበር ችሎት ይህንን የተወሳሰበ የሕግ ጥያቄ ለመፍታት የተጠቀሱትን ቀደምት አስገዳጅ ውሳኔዎችን በመመርመር ለእያንዳንዳቸው ተገቢ ነው ያለውን ማብራሪ ሰጥቶባቸዋል፡፡ በመጀመሪያ በሰ/መ/ቁጥር 43600 የተሰጠውን አስገዳጅ የህግ ትርጉምን አልሻረውም፤ ይልቁንም ጉዳዩ መኖሪያ ቤትን የሚመለከት በመሆኑና መኖሪያ ቤት ላይ የባለቤትነት መብት ስላለ፣ ትንታኔው ከዚህ መዝገብ ጋር በቀጥታ እንደማይገናኝ በማስረዳት የጉዳዩን ልዩነት (Distinguishing) በማሳየት ትርጉሙ እንዲፀና አድርጎታል፡፡ በመቀጠልም በሰ/መ/ቁጥር 69302 ለገጠር መሬት የተሰጠውን የ10 ዓመት ይርጋ አስገዳጅ የህግ ትርጉም ትክክለኛነት የተቀበለ ቢሆንም፣ ይህንን የገጠር መሬት ቀደመት አስገዳጅ ትርጉም በቀጥታ በከተማ መሬት ላይ መተግበሩ ስህተት መሆኑን በማሳየት የስር ፍርድ ቤትን አካሄድ ነቅፏል፡፡ በመጨረሻም በሰ/መ/ቁጥር 210477 የተሰጠውን አስገዳጅ የህግ ትርጉም ሙሉ በሙሉ የሻረው ሲሆን ለውሳው ምሶሶ ያደረጋቸው አበይት ምክንያቶቹም የቀደመው አስገዳጅ የህግ ትርጉም የባለቤትነት መብትን እና የይዞታ መብትን በማምታታት፣ በመሬት ይዞታ መብት ላይ ሊቀርብ የማይችለውን የመፋለም ክስ የይርጋ መቃወሚያ በከተማ መሬት ይዞታ ላይ ተግባራዊ ማድረግ አይቻልም የሚሉት መሆናቸውን አዲሱ ትርጉም በግልጽ አስቀምጧል፡፡
ችሎቱ አዲሱን የሕግ ትርጉም ለመስጠትና ለመተንተን የተከተለው አመክንዮ አራት ደረጃዎችን ያካተተ ነበር፡፡ አንደኛ ትንታኔውን በሕገ-መንግስቱ አንቀጽ 40(3) ላይ በማስረፅ መሬት የግለሰብ ባለቤትነት ሊኖርበት የማይችል መሆኑን እና የፍ/ብ/ሕ/ቁ 1206 የመፋለም ክስ መሬት ላይ ተፈፃሚ እንደማይሆን አረጋግጧል፡፡ ሁለተኛ በከተማ መሬት ይዞታ ላይ የሚኖረው መብት (በሊዝም ሆነ በነባር) በነገር ላይ ያለ (In rem) ተጨባጭ የንብረት መብት እንጂ ተራ የኪራይ ውል ግንኙነት አለመሆኑን በማብራራት የመብቱን ህልውና ገልጿል፡፡ ሦስተኛ የሲቪል ሎው (Civil Law) የመፋለም ክስ ፅንሰ-ሐሳብ እና የኮመን ሎው (Common Law) የማስለቀቅ ክስ (Action of ejectment) ፅንሰ-ሐሳቦችን በማነፃፀር፣ ምንም እንኳን ይህ የኮመን ሎው አሠራር ለሕግ ሥርዓታችን እንግዳ ቢሆንም፣ በሕግ የታወቀ መብት እስካለ ድረስ ስያሜው ክሱን ለማስተናገድ እክል እንደማይሆን አብራርቷል፡፡ አራተኛ የሕግ ክፍተቱን ለመሙላት (Gap-filling) የፍ/ብ/ሕ/ቁ 1677(2) ድንጋጌን ድልድይ በማድረግ በፍ/ብ/ሕ/ቁ 1845 ሥር የተቀመጠውን አጠቃላይ የ10 ዓመት ይርጋ በከተማ መሬት ይዞታ ላይ ተግባራዊ አድርጓል፡፡ በዚህም መሠረት
የከተማ መሬት ይዞታን አላግባብ ከያዘ ሰው ላይ ለማስመለስ የሚቀርብ ክስ በአስር ዓመት ይርጋ ይታገዳል የሚል አዲስ አስገዳጅ የሕግ ትርጉም ሰጥቷል፡፡
ክፍል አምስት፡ ተግባራዊ የተደረጉት የፍትሐብሔር ሕግ ድንጋጌዎች ትንታኔ
በዚህ ውሳኔ ተግባራዊ የተደረገው የፍ/ህ/ቁ 1845 "በውል ስለሚመነጩ ግዴታዎች" ሥር የሚገኝ ሲሆን፣ ውልን ስለመፈፀም፣ ባለመፈፀም እና ውልን ስለማፍረስ የሚቀርቡ ክሶች በአስር ዓመት ይርጋ እንደሚታገዱ የሚደነግግ ነው፡፡ የመሬት ይዞታ ክርክር ደግሞ በባህሪው ከውል የሚመነጭ ሳይሆን ከሕገ-ወጥ ይዞታ ወይም ንጥቂያ የሚመነጭ ነው፡፡ ሆኖም ችሎቱ ይህንን ክፍተት ያገናኘው የፍ/ብ/ሕ/ቁ 1677(2) ድንጋጌን በዋቢነት በመጥቀስ ሲሆን ይህ ድንጋጌ የውል ደንቦች ከውል ውጭ በሆኑ ግዴታዎች ላይ ተፈፃሚ እንደሚሆኑ ይደነግጋል፡፡ ይሁን እንጂ ሕገ-ወጥ የመሬት ያዥ ያለበት "ግዴታ" ምን ዓይነት እንደሆነ (ከሕገ-ወጥ ድርጊት ወይስ ያለአግባብ ከመበልፀግ የመነጨ መሆኑን) ችሎቱ በግልጽ አላብራራም፡፡ እንዲሁም በፍ/ህ/ቁ 1846 መሠረት የይርጋው መቆጠር መነሻ ጊዜ ከመቼ እንደሚጀምር፣ በአንቀጽ 1851 መሠረት የይርጋ መቋረጥ እንዴት እንደሚስተናገድ፣ እና በፍ/ህ/ቁጥር 1854 መሠረት መጥፎ ልቦና (Bad faith) ያለው ሰው እንኳን በይርጋው መጠቀም የሚችል መሆኑ በመሬት ንጥቂያ ላይ የሚያመጣው ህጋዊ ውጤት/ ተፅዕኖ መኖር ያለመኖሩን በችሎቱ ትንታኔ ሥር በሰፊው ያልተዳሰሱ ግን መሰረታዊ የሆኑ የህግ ጥያቄዎች ሆነው አልፈዋል፡፡
ክፍል ስድስት፡ ስለ አዲሱ ትርጉም ጥንካሬዎች
የሰባት ዳኞች ችሎት የሰጠው ይህ ውሳኔ በኢትዮጵያ የንብረት ሕግ ስነ ህግ ዕድገት ላይ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ያላቸው በርካታ ጥንካሬዎችን ይዟል፡፡ በመጀመሪያ ደረጃ ችሎቱ የፍትሐብሔር ሕጉን እና የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ሕገ-መንግሥትን የመሬት መብት ስሪት በአግባቡ በማዋሃድ የግል ባለቤትነትን እና የመሬት ይዞታ መብትን በጥልቀት ለመለየት መቻሉ ሊደነቅ የሚገባው ሕገ-መንግሥታዊ ትንታኔ ነው፡፡ በተጨማሪም በሰ/መ/ቁጥር 43600 የተሰጠውን አስገዳጅ የህግ ትርጉምን ሙሉ በሙሉ ከመሻር ይልቅ በሚገባው የሕግ አውድ (በቤት ባለቤትነት ላይ) ብቻ እንዲወሰን በማድረግ ትክክለኛ የአስገዳጅ የህግ ትርጉም አስተዳደር/አተገባበርን ለማሳየት ችሏል፡፡ እንዲሁም የባለቤትነትን እና የይዞታ መብትን ማምታታት በሰ/መ/ቁጥር 210477 የተሰጠውን መሠረታዊ የሕግ ስህተት ያለበትን አስገዳጅ የህግ ትርጉም በአግባቡ በማረም ለአስገዳጅ የሕግ ትርጉም ስርዓት ጥራት እና ታዓማኒነት አስተዋጽኦ አድርጓል፡፡ ችሎቱ የከተማ መሬት መብቶችን ተራ የውል ግንኙነት ሳያደርግ ከሁሉም ሰዎች ልንጠይቃቸው የምንችላቸው ተጨባጭ መብቶች (In rem) መሆናቸውን ማረጋገጡ እና ጉዳዩን በ7 ዳኞች በማየት ተቋማዊ ቅቡልነትነን (Institutional Legitimacy) ማጠናከሩ የውሳኔው ዐበይት ጥንካሬዎች ናቸው፡፡
ክፍል ሰባት፡ አዲሱ አስገዳጅ የሰበር ውሳኔ እና አዋጅ ቁጥር 1324/2016፡ የሕግ በጊዜ አተገባበር እና የአመሳስሎሽ ትርጓሜ መነጽር የተደረገ ዳሰሳ
7.1 መግቢያ
የካቲት 30 ቀን 2018 ዓ.ም. ሰባት ዳኞች በተሰየሙበት የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት የተሰጠው አስገዳጅ ውሳኔ ቁልፍ ትርጉሙ (Ratio decidendi)፤ የከተማ መሬት ይዞታን ሕገ-ወጥ ከሆነ መንገድ ከያዘው ሰው ላይ ለማስመለስ የሚቀርብ ክስ በ10 ዓመት ይርጋ ይታገዳል የሚለው ሲሆን ፣ "የሕግ በጊዜ አተገባበር" (Intertemporal law፤ ሕጎች በጊዜ ሂደት ያላቸውን ተፈፃሚነት የሚገዛ መርህ) እና "የአመሳስሎሽ ትርጓሜ" (Analogical reasoning) ተቀራራቢ የሕግ ድንጋጌዎችን በመጠቀም የሕግ ክፍተትን የመሙላት ሥነ-ዘዴ) በሚሉት ሁለት መነጽሮች ሲመረመር እጅግ አሳማኝ የሆኑ አካዳሚያዊ እና ተግባራዊ ጥያቄዎችን ሊስነሳ የሚችል ነው፡፡ ይህ አዲስ አስገዳጅ ውሳኔ እና ከእርሱ በፊት ነሐሴ 8 ቀን 2016 ዓ.ም የወጣው የፌዴራል የገጠር መሬት አስተዳደርና አጠቃቀም አዋጅ ቁጥር 1324/2016. መገጣጠም፣ የችሎቱን ሥነ-ሥርዓታዊ ትክክለኛነት እና የፅንሰ-ሐሳብ (የዶክትሪን) ምርጫዎች ለየብቻ እና በሂሳዊ መንገድ እንድንገመግም ሰፊ የትንታኔ መደላድል የሚፈጥር ይመስለኛል፡፡ በዚህ ረገድ ሊደረግ የሚችለው ትንታኔ የጉዳዩን ፍሬ-ነገሮች፣ የአዋጅ ቁጥር 1324/2016 ድንጋጌ አግባብነት ያላቸውን ድንጋጌዎች (በተለይም የይርጋ እና የሽግግር ድንጋጌዎችን)፣ እና የፍትሐብሔር ሕጉን የይርጋ ማዕቀፍ መሠረት በማድረግ ሊከናወን የሚችል ነው፡፡
በሌላ በኩል ውሳኔው አንዳንድ ድክመቶች እና ቀጣይ ማብራሪያ የሚሹ ክፍተቶችም የሚታዩበት መሆኑን የግል ምልክታ አድርጌአለሁ፡፡ የፍ/ብ/ሕ/ቁ 1845 የ10 ዓመት ይርጋ በከተማ መሬት ላይ ተግባራዊ እንዲሆን የተሰጠው ትንታኔ አጠር ያለ እና ተጨማሪ ማብራሪያ የሚሻ ነው፡፡ ይህንን ይርጋ ተግባራዊ ማድረግ በተለይም ከአገር ውጭ በነበሩ ወይም በተለያዩ አቅም በሚያሳጡ ሁኔታዎች ውስጥ ላሉ ዜጎች ሕገ-መንግሥታዊ መብት ላይ የሚያመጣው ተፅዕኖ ከፖሊሲ አኳያ አልተገመገመም፡፡ እንዲሁም በሰ/መ/ቁጥር 43600 የተሰጠውን የህግ ትርጉምን በተመለከተ "ተፈፃሚ ለማድረግም ሆነ ተቃርኖ አለው ለማለት አልተቻለም" የሚለው የችሎቱ አገላለጽ የተወሰነ ብዥታን የሚፈጥርና ይበልጥ ግልጽ ቢደረግ ይመረጥ የነበረ ነው፡፡ በዚሁ አስገዳጅ ውሳኔ ውስጥ በሌሎች ልዩ ህጎች የተመለከቱትን የይርጋ ድንጋጌዎችን በሚመለከት የተቀመጠውን አገላለፅ መጠቀም ያልተቻለበትን አግባብ ውሳኔው አያሳይም፡፡ ከዚህም በተጨማሪ የመፋለም ክስ ከመሬት ጋር እንደማይሄድ ከተገለጸ በኋላ፣ በትክክል ክሱ በምን ዓይነት የክስ ምክንያት (Cause of action) መቅረብ እንዳለበት ግልጽ አቅጣጫ አለመቀመጡ ለባለሙያዎች ክፍተት ትቷል፡፡ ከገጠር መሬት አዋጅ ድንጋጌዎች ጋር በማነፃፀር ለከተማ መሬት ተመሳስሎሽ ትንታኔ (Analogical reasoning) ያልተጠቀመበትን አግባብም መኖሩን ውሳኔው ማሳየቱን ችሎቱ እንዲህ አይነት የህግ ትርጉም ስልት ተግባር ላይ ለማዋል/ለመውሰድ የነበረውን መልካም አጋጣሚ ማምከኑን የሚያሳይ ነው፡፡ እንዲሁም ቅን ልቦ የሌለው ወይም መጥፎ ልቦና (Bad faith) ያለው የመሬት ነጣቂ የ10 ዓመት ይርጋን ተገን አድርጎ መብት ሊያገኝ የሚችልበትን የፍ/ህ/ቁጥር 1854 ድንጋጌ አንድምታ ችሎቱ አለመመርመሩ እንደ ውሳኔው ድክመቶች ሊነሱ የሚችሉ ነጥቦች ይመስሉኛል፡፡
7.2 አዲሱን ሕግ በመታየት ላይ ባሉ ጉዳዮች ላይ ያለመተግበር ትክክለኛነት፡ የሽግግር ድንጋጌዎችን በጥብቅ መከተል
ከላይ እንደተጠቀሰው በፍ/ብ/ህ/ሥ/ሥርዓት እና በሕግ ትርጓሜ መሠረታዊ መርሆች መሠረት፣ አዲስ የወጣ መሰረታዊ ሕግ (Substantive law) የሕግ አውጪው በግልጽ ካልደነገገ በስተቀር ወደኋላ ተመልሶ አይሰራም፡፡ ይህ ሕግ ወደኋላ ተመልሶ አለመሥራት መርህ (lex prospicit, non respicit) የሕግ ተገማችነት (Legal certainty) የጀርባ አጥንት ሲሆን፣ የተከራካሪ ወገኖች መብት እና ግዴታ የሚገዛው ድርጊቱ በተፈጸመበት ወይም ቢያንስ ክርክሩ በፍርድ ቤት በተጀመረበት ጊዜ በነበረው ሕግ መሆኑን ያረጋግጣል፡፡ አሁን በተያዘው ጉዳይ ይህ መርህ እጅግ ግልጽ በሆነ መንገድ ይሠራል፡፡ ተጠሪ (ከሳሽ) ክሳቸውን ያቀረቡት ሐምሌ 14 ቀን 2013 ዓ.ም.
ሲሆን፣ የክሱ መነሻ (ሕገ-ወጥ የመሬት ይዞታ ንጥቂያ) ተከሰተ የተባለው ደግሞ በ2011 ዓ.ም. (ወይም አመልካች እንደሚሉት በ1980 ዓ.ም.) ነው፡፡ በአንፃሩ አዲሱ የገጠር መሬት አስተዳደርና አጠቃቀም አዋጅ ቁጥር 1324/2016 ፀድቆ በነጋሪት ጋዜጣ ታትሞ የወጣው በነሐሴ 08 ቀን 2016 ዓ.ም. ነው፡፡ ይህም ማለት ክርክሩ ከተጀመረና በተለያዩ የፍርድ ቤት እርከኖች ሲንከባለል ከቆየ ከዓመታት በኋላ ነው፡፡ ዋናው ቁም ነገር አዋጁ ራሱ ይህንኑ ሁኔታ የሚገዛ ግልጽ የሽግግር ድንጋጌ (Transitional provision) የያዘ መሆኑ ነው፡፡ የአዋጅ ቁጥር 1324/2016 አንቀጽ 65(1) በማያሻማ ቋንቋ እንዲህ ይደነግጋል፡- "የዚህ ሕግ ድንጋጌዎች ይህ አዋጅ ከመፅደቁ በፊት… ፍርድ ቤት ቀርበው ክርክር እየተደረገባቸው ባሉ ጉዳዮች ላይ ተፈፃሚ አይሆንም"፡፡ ይህ ድንጋጌ አዲሱ ሕግ፤ በአዋጁ የተካተቱ ማናቸውንም የይርጋ ጊዜያት ጨምሮ፣ ወደፊት ብቻ የሚሠራ እንጂ አዋጁ ከመውጣቱ በፊት በፍርድ ቤት በመታየት ላይ የነበሩ ጉዳዮችን ወደኋላ ተመልሶ እንደማያካትት የሕግ አውጪው የሰጠው ግልጽ መመሪያ ነው፡፡
ይህ የሽግግር ድንጋጌ በቀጥታ አግባብነት ያለው፣ የዚሁ አዋጅ አንቀጽ 64(2) ለመሬት ማስለቀቅ ክስ የ15 ዓመት የይርጋ ጊዜ ስለሚደነግግ ነው፡፡ ይህ ድንጋጌ ለዚህ ጉዳይ ተፈፃሚነት ቢኖረው ኖሮ ውጤቱን ሊቀይረው ይችል ነበር፡- ማለትም ፍርድ ቤቱ በተገበረው የ10 ዓመት ይርጋ ታግዷል የተባለው የተጠሪ ክስ፣ የይርጋው መቆጠር መነሻ ጊዜ አሰላል ታይቶ በ15 ዓመቱ የይርጋ ጊዜ ሥር ሊድን (ሊቀጥል) ይችል ነበር፡፡ ሆኖም ሰባት ዳኞች የተሰየሙበት የሰበር ችሎት ይህንን አዲስ የ15 ዓመት የይርጋ ጊዜ ከ2013 ዓ.ም. ጀምሮ በፍርድ ቤት በመታየት ላይ ባለ ጉዳይ ላይ ተግባራዊ አለማድረጉ ፍፁም ትክክል ነው ሊባል የሚችል ነው፡፡ እንዲያውም በሥነ-ሥርዓት ደረጃ ሲታይም አስገዳጅነት የነበረው ተግባር ነው፡፡ ይህን አድርጎ ቢሆን ኖሮ፣ አጠቃላይ የሆነውን ሕግ ወደኋላ ተመልሶ አለመሥራት መርህን እና የአንቀጽ 65(1)ን የተለየ የሽግግር መመሪያ በጣሰ ነበር፡፡
ስለሆነም ችሎቱ የሕግ ክፍተቱን ለመሙላት የተከተለው አካሄድ መገምገም ያለበት ክሱ በቀረበበት ጊዜ (በ2013 ዓ.ም.) በነበረው የሕግ ማዕቀፍ ውስጥ ሆኖ ነው፡፡ በዚያን ወቅት፣ የከተማ መሬት ይዞታን ለማስመለስ የሚቀርብ ክስን በተመለከተ የተለየ የይርጋ ጊዜ ባለመኖሩ የተፈጠረውን የሕግ ክፍተት ለመሙላት በሕግ ሥርዓቱ ውስጥ የነበሩት አማራጮች፣ የፍትሐብሔር ሕጉ (በተለይም አንቀጽ 1677 እና 1845)፣ ወይም ደግሞ ቀድሞ የነበረው የገጠር መሬት አዋጅ (አዋጅ ቁጥር 456/1997) ብቻ ነበሩ (የኋለኛው አዋጅም ቢሆን በሰበር መ/ቁ 69302 እንደተረጋገጠው ለዚህ ክስ የሚሆን ግልጽ የይርጋ ጊዜ አላስቀመጠም ነበር)፡፡ ችሎቱ ክፍተቱን ለመሙላት የፍ/ህ/ቁ 1677(2) እና 1845ን (ጠቅላላ የ10 ዓመት ይርጋን) የመረጠ ሲሆን፣ ይህ ምርጫ የተደረገው በወቅቱ በነበረው የሕግ ሥርዓት ተጨባጭ ሁኔታ ላይ ተመሥርቶ ነው፡፡ የሕግ አውጪው ከጊዜ በኋላ ለገጠር መሬት ክሶች የተለየ እና የረዘመ የይርጋ ጊዜ ማውጣቱ የችሎቱን ውሳኔ ወደኋላ ተመልሶ ሕገ-ወጥ አያደርገውም፡፡ ይልቁንም፣ ፍርድ ቤቱ ገና ላልወጣ ሕግ እውቅና ሰጥቶ ወደኋላ ተግባራዊ አለማድረጉ የዳኝነት ሥልጣን ያለበትን የጊዜ ገደብ መረዳቱን እና የሕግ አውጪውንና የሕግ ተርጓሚውን የሥልጣን ክፍፍል ማክበሩን ያሳያል፡፡ በመሆኑም ባለሰባት ዳኞች ሰበር ችሎት የሕግን በጊዜ አተገባበር (Intertemporal law) መርህ የተገበረበት መንገድ ጉድለት የለሽ ነው፡፡ ችሎቱ አግባብነት ያለውን የጊዜ ማዕቀፍ በትክክል ለይቷል፤ ክሱ በቀረበበት ጊዜ የነበረውን ሕግ ተግብሯል፤ እንዲሁም ከዓመታት በኋላ የሚወጣን ሕግ አስቀድሞ ከመገመትና ከመተግበር ታቅቧል ለማለት ያስደፍራል፡፡
7.3 የአመሳስሎሽ ትርጓሜ ችግር፡ የሕግ ክፍተትን ለመሙላት በተመረጠው ምንጭ ላይ የታየ የፅንሰ-ሐሳብ (የዶክትሪን) መዛባት
ምንም እንኳን ችሎቱ የሕግን በጊዜ አተገባበር መርሆችን የተከተለበት መንገድ ተገቢነት ያለው ቢሆንም፣ የሕግ ክፍተቱን ለመሙላት የመረጠው የአመሳስሎሽ (Analogical) ድልድይ ግን ቀጣይነት ያለው አካዳሚያዊ ክርክር የሚሻ ከባድ የሕግ ፍልስፍና ጥያቄን ማስነሳቱ አይቀሬ መስሎ ታይቶኛል፡፡የዚህ ሂሳዊ ግምገማዬ መነሻም ችሎቱ የሕግ ክፍተቱን ለመሙላት (Gap-filling) ጥረት ማድረጉ አይደለም፤ ለከተማ መሬት ክስ የተለየ ይርጋ ባለመኖሩ ይህን ማድረጉ ተገቢና አስፈላጊ ነበር፣ ነገር ግን ትችቱ የሚያነጣጥረው በአመሳስሎሽ የወሰደውን የይርጋ ጊዜ ባመጣበት የተለየ ምንጭ ላይ በማተኮር ነው፡፡ ችሎቱ የከተማ መሬት ይዞታ ክርክርን የሚገዛ የይርጋ ጊዜ በሕግ አለመኖሩን ሲገነዘብ፣ ከፍትሐብሔር ሕጉ ሦስተኛ መጽሐፍ (ስለ ንብረት ሕግ) በመውጣት፣ ወደ አራተኛው መጽሐፍ (ስለ ግዴታዎች) ተሻገረ። በዚያም የውል ሕግ ደንቦች ከውል ውጭ በሆኑ ግዴታዎች ላይ ተፈፃሚ እንደሚሆኑ የሚደነግገውን አንቀጽ 1677(2) ድንጋጌን እንደ ማሻገሪያ ድልድይ በመጠቀም በፅሑፍ አቀማመጡ ውልን ለመፈፀም፣ ላለመፈፀም ወይም ለማፍረስ ለሚቀርቡ ክሶች የተዘጋጀውን በቁጥር 1845 ድንጋጌ ሥር የሚገኘውን አጠቃላይ የ10 ዓመት ይርጋ ተግባራዊ አድርጎታል። ይህ አካሄድ ከዚህ ቀደም ለገጠር መሬት ክርክሮች በሰበር መ/ቁ 69302 ከተወሰደው የትንታኔ መንገድ ጋር ሙሉ በሙሉ ተመሳሳይ ነው፡፡
ሆኖም የሕግ አውጪው በገጠር መሬት አስተዳደርና አጠቃቀም አዋጅ ቁጥር 1324/2016 የገጠር መሬትን ለማስመለስ የሚቀርብ ክስን የይርጋ ጊዜ በተመለከተ በራሱ ጊዜ ምላሽ ሲሰጥ፣ በአንቀጽ 64(2) ሥር ያስቀመጠው ገደብ 15 ዓመት እንጂ 10 ዓመት አልነበረም፡፡ ይህ የሕግ አውጪው ምርጫ በፅንሰ-ሐሳብ ደረጃ እጅግ ወሳኝ ነው፤ ምክንያቱም ለመሬት ማስለቀቅ ክሶች ተገቢ ነው ብሎ ያሰበው የጊዜ አድማስ ፍርድ ቤቱ በአመሳስሎሽ ከመረጠው የጊዜ ገደብ በእጅጉ የተለየ መሆኑን ያሳያልና፡፡ ከዚህም በላይ፣ የሕግ አውጪው የ15 ዓመትን ጊዜ መምረጡ የዘፈቀደ አልነበረም፡፡ ይህ ጊዜ በፍትሐብሔር ሕጉ አንቀጽ 1168 ሥር የማይንቀሳቀስ ንብረትን በተከታታይ ይዞታ እና ግብር በመክፈል (Adverse possession) ባለሀብት ለመሆን ከሚያስፈልገው የ15 ዓመት ጊዜ ጋር በትክክል ይገጠማል፡፡ ይህ መመሳሰል በግልጽ የሚያሳየው፣ የሕግ አውጪው የመሬት ማስለቀቅ ክስ ይርጋን ከንብረት ሕጉ የይዞታ መብት አሰጣጥ ጋር በማዛመድ (Calibrating) በንብረት መብት ማዕቀፍ ውስጥ ውስጣዊ ወጥነትን መፍጠሩን ነው፡፡
ይህ ምልከታ አንድ መሠረታዊ የስነ-ዘዴ (Methodological) ጥያቄን ቁልጭ አድርጎ ያጋልጣል፡፡ ይኸውም ችሎቱ የከተማ መሬት ማስለቀቅ ክስን (ወደ አንቀጽ 1168 የ15 ዓመት ይርጋ ከሚያመላክተው) የንብረት ሕግ አሠራር ይልቅ፣ (በአንቀጽ 1845 ወደ 10 ዓመት የሚያወርደው) የውል ግዴታ ጋር ማመሳሰል ለምን መረጠ? ጥያቄው አካዳሚያዊ ብቻ አይመስለኝም፡፡ በሲቪል ሎው የሕግ ሥነ-ዘዴ መሠረት፣ አንድ ፍርድ ቤት በአመሳስሎሽ ትርጓሜ የሕግ ክፍተትን ሲሞላ፣ አመሳስሎሹ መወሰድ ያለበት በጣም የጠበቀ የቅርብ ዝምድና ካለው የሕግ ማዕቀፍ (Nearest cognate legal regime)፣ ማለትም በውስጣዊ መርሆች፣ ዓላማዎች እና መዋቅር ከዋናው ጉዳይ ጋር እጅግ ከሚቀራረበው የሕግ
አካል ሊሆን እንደሚገባው ይታወቃል፡፡ የመሬት ይዞታ መብት (Holding rights)፣ የሰባት ዳኞች ችሎት ራሱ እንዳመነው፣ ተጨባጭ፣ የሚመዘገቡ፣ የሚተላለፉ እና መያዣ ሊሆኑ የሚችሉ፣ ከሁሉም ስዎች ልንጠይቃቸው የምንችላቸው (In rem) የንብረት መብቶች ናቸው፡፡ እነዚህ መብቶች ከግለሰቦች ጋር ብቻ ከሚያያዙ (Personal, inter partes) እና ፍጹም የተለየ መርህ ካላቸው የውል ግዴታዎች ጋር በመደባቸው አይገናኙም፡፡ አንድ ሕገ-ወጥ የመሬት ያዥ መሬቱን የመመለስ ግዴታ ያለበት፣ በነገር ላይ ያለን (In rem) መብት በመጣሱ እንጂ የውል ቃልን በማፍረሱ (Breach of contractual promise) አይደለም፡፡
ይህ የሕግ ባህሪ ታሳቢ ሲደረግ፣ ይበልጥ ፅንሰ-ሐሳባዊ ወጥነት (Doctrinal coherence) ያለው የአመሳስሎሽ ምንጭ ሊሆን የሚገባው የፍትሐብሔር ሕጉ የንብረት ድንጋጌዎች፤ በተለይም በአንቀጽ 1168 ሥር ያለው የ15 ዓመት ማዕቀፍ እንጂ የአራተኛው መጽሐፍ የውል ግዴታዎች ክፍል አልነበረም፡፡ የፍ/ህ/ቁ 1168 ድንጋጌ የማይንቀሳቀስ ንብረትን ለ15 ዓመት ከነግብሩ የያዘ ሰው የንብረቱ ባለቤት እንደሚሆን ይደነግጋል፡፡ ከዚህ በተቃራኒው በኩል ያለውን አመክንዮ ስናይ (ከመብቱ ለተነጠቀው ሰው አኳያ)፣ ንብረቱን በሕገ-ወጥ መንገድ የተነጠቀ ሰው መብቱን ለማስመለስ የሚችለውም በተመሳሳይ የ15 ዓመት ጊዜ ውስጥ መሆን አለበት የሚል መደምደሚያ ላይ ያደርሳል፡፡ ይህ ሚዛናዊ የሆነን ማዕቀፍ ይፈጥራል፡፡ በሌላ አገላለፅ ሕገ-ወጥ ያዡ መብት ለማግኘት 15 ዓመት ያስፈልገዋል፤ መብቱ የተነጠቀው ሰው ደግሞ መብቱን ለማስመለስ 15 ዓመት አለው ማለት ነው፡፡ በአንፃሩ ሰበር ችሎቱ የ10 ዓመቱን የውል ይርጋ መተግበሩ መዋቅራዊ አለመመጣጠንን (Asymmetry) የሚፈጥር ነው፡፡ ምክንያቱም ሕገ-ወጥ ያዡ ባለመብት ለመሆን አሁንም በአንቀጽ 1168 መሠረት 15 ዓመት ሲያስፈልገው፣ መብት የተነጠቀው ሰው ግን ከንብረት ሕጉ መዋቅር ጋር ምንም ዓይነት መዋቅራዊ ዝምድና በሌለው ሕግ መብቱን በ10 ዓመት ብቻ ያጣል የሚል መልዕክት አለው ማለት ነው፡፡
የሕግ አውጪው ከጊዜ በኋላ በአዋጅ ቁጥር 1324/2016 አንቀጽ 64(2) መሠረት ለገጠር መሬት ክስ የ15 ዓመት ይርጋ ማውጣቱ፣ ከላይ ለተነሳው ሂሳዊ ትንታኔ ከፍ ያለ ዋጋ ያለውን የማጠናከሪያ ድጋፍ የሚሰጥ ሁኖ ይገኛል፡፡ ምንም እንኳን ችሎቱ የሕግ አውጪውን ቀጣይ ውሳኔ አስቀድሞ ማወቅ ባይችልም፣ የሕግ አውጪው የወሰደው ምርጫ ግን ለመሬት ማስለቀቅ ክርክሮች ትክክለኛው የፅንሰ-ሐሳብ (የዶክትሪን) መሠረት የፍ/ህ/ቁጥር 1168 ድንጋጌ የንብረት ሕግ አመክዮ እንጂ የቁጥር 1845 ድንጋጌ የውል ሎጂክ አለመሆኑን ያረጋግጣል፡፡ የሕግ አውጪው የይርጋ ሥርዓቱን ከውል ይልቅ ከንብረት ሕግ ማዕቀፍ ጋር ማጣመሩ የሚያሳየው፣ የችሎቱ የአመሳስሎሽ ድልድይ በፅሑፋዊ ትርጓሜ ሊደገፍ የሚችል ቢሆንም በፅንሰ-ሐሳብ (በዶክትሪን) ደረጃ ግን አጥጋቢ አለመሆኑን (Doctrinally suboptimal) ነው፡፡
በመሆኑም አዲሱ አስገዳጅ የሰበር ውሳኔ (ለከተማ መሬት ክስ የ10 ዓመት ይርጋን ማስቀመጡ) እና ከእርሱ በፊት የወጣው አዋጅ ቁጥር 1324/2016 (በአንቀጽ 64(2) ለገጠር መሬት ክስ የ15 ዓመት ይርጋን መደንገጉ) መገጣጠም፣ በኢትዮጵያ የመሬት ሕግና የአስገዳጅ የህግ ትርጉም ላይ ያልታሰበ እና ከፍተኛ አንድምታ ያለው የይርጋ ጊዜ መከፈል (Bifurcation of limitation periods) ይዞ ተከስቷል፡፡ ከዚህ አንፃር አሁን በተጨባጭ ባለው ነባራዊ የሕግ ማዕቀፍ መሠረት፡-የይዞታ መብቱ በሕገ-ወጥ ያዥ የተጣሰበት የገጠር መሬት ባለይዞታ፣ መብቱን ለማስመለስ የሚያስችል የ15 ዓመት ጊዜ አለው (በአዋጅ 1324/2016 አንቀጽ 64(2) መሠረት) ሲኖረው ፍጹም ተመሳሳይ በሆነ ሁኔታ ውስጥ የሚገኝ የከተማ መሬት ባለይዞታ ግን በአዲሱ የሰበር ውሳኔ እና በፍ/ብ/ሕ/ቁ 1677(2) እና 1845 ደንጋጌዎች መሠረት የ10 ዓመት ጊዜ ብቻ ይኖረዋል ማለት ነው፡፡
ይህን ልዩነት በጠንካራ መርህ ላይ ተመሥርቶ ለማስረዳትና አሳማኝ ለማድረግ እጅግ አዳጋች ነው፡፡ ምክንያቱም የገጠርም ሆነ የከተማ መሬት ይዞታ መብቶች የሚመነጩት ከአንድ ዓይነት ሕገ-መንግሥታዊ መሠረት፤ ማለትም መሬት (የገጠርም ሆነ የከተማ) የመንግስትና የሕዝብ ንብረት መሆኑን ከሚያውጀውና የግል ባለቤትነትን ከሚከለክለው የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ሕገ-መንግሥት አንቀጽ 40(3) ነውና፡፡ የመብቱ ባህሪ (ከባለቤትነት ያነሰ ነገር ግን በነገር ላይ ያለ ከሁሉም ሰዎች ልንጠይቀው የምንችለው (In rem) ተጨባጭ የንብረት መብት መሆኑ) መሬቱ የሚገኘው በከተማ ክልል ውስጥ ሆነም በገጠር፣ በተጠቃሹ ሕገ-መንግሥታዊ ድንጋጌ ዕይታ አንድ ዓይነት ነው፡፡
የሕገ-መንግሥታዊ መሠረቱ አንድ ዓይነት ከሆነ፣ ለባለይዞታዎች የሚሰጠው የሕግ ከለላም በመርህ ደረጃ አንድ ዓይነት ሊሆን ይገባል፡፡ ለገጠር መሬት ባለይዞታ 15 ዓመት እየተሰጠ የከተማውን ባለይዞታ በ10 ዓመት መገደብ ምክንያታዊ የሆነ የፖሊሲ መሠረት (Rational policy basis) የሌለው ልዩነትን መፍጠር ሲሆን፣ ይህ ደግሞ ሰባት ዳኞች የተሰየሙበት ችሎት የተቃረኑ ውሳኔዎችን በማረም ሊያመጣው የፈለገውን የሕግ ወጥነት (Doctrinal consistency) የሚሸረሽር ነው፡፡
አንድ ሰው የከተማ እና የገጠር መሬት የተለያዩ ማሕበራዊና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳዎች እንዳላቸው፣ በተለያዩ የቁጥጥር ሥርዓቶች እንደሚመሩ፣ እና የክርክሮቹም ተጨባጭ ሁኔታዎች እንደሚለያዩ በማንሳት፣ ይህ ልዩነት የተለያየ የይርጋ ጊዜን ተገባራዊ ማድረግ እንደሚችል ይሞግት ይሆን ይሆናል፡፡ ይሁን እንጂ እንዲህ ዓይነቱ መከራከሪያ፣ የከተማ መሬት የይዞታ ሥርዓት ከገጠሩ ይበልጥ መደበኛ፣ በሰነድ የተደገፈ፣ እና በአስተዳደር ሥርዓት የተደራጀ ነው የሚለውን መደበኛ አስተሳሰብ ወደ ጎን ትቶ፣ የከተማ ባለይዞታ መብቱን ለመጠየቅ ከገጠሩ ባለይዞታ ያነሰ ጊዜ ሊሰጠው የሚገባው ለምንድን ነው? የሚለውን አሳማኝ በሆነ መንገድ ማስረዳት ይጠበቅበታል፡፡ እንዲያውም፣ በገጠር መሬት ይዞታ ላይ ያለው ሰፊ ኢ-መደበኛነት እና የሰነድ አያያዝ ክፍተት፣ መረጃዎች በገጠሩ አካባቢ ቶሎ ስለሚጠፉ፣ ለገጠር መሬት ክስ ከከተማው ያጠረ (ያልረዘመ) የይርጋ ጊዜ ሊያስፈልግ ይችላል ወደሚል ንድፈ-ሐሳባዊ መከራከሪያ ሊያመራን ይችላል፡፡ አሁን በህጉና በአስገዳጅ የህግ ትርጉም የተወለደው ዥንጉርጉር ሥርዓት ማለትም ገጠር 15 ዓመት፣ የከተማ 10 ዓመት ይርጋ ጊዜ እንዲሆን የተደረገበት ኩነት ይህንን ሎጂክ/አመክንዮ/ የተገላቢጦሽ ያደርገዋል፡፡
7.4 የክፍል 7 ጥማቂ
የሰባት ዳኞች ችሎት በዚህ ጉዳይ ላይ የሕግን በጊዜ አተገባበር (Intertemporal law) ያስተናገደበት መንገድ እንከን የለሽ (Flawless) ነው ሊባል የሚችል ቢሆንም ችሎቱ ክሱ በቀረበበት ጊዜ (በ2013 ዓ.ም.) የነበረውን የሕግ ማዕቀፍ በመተግበር፣ የሕግ ክፍተቱን በወቅቱ በነበሩ የፍትሐብሔር ሕግ ድንጋጌዎች በመሙላት፣ እና ገና ፀድቆ ላልወጣ አዋጅ (አዋጅ ቁጥር 1324/2016) ወደኋላ ተመልሶ የሚሠራ የተፈፃሚነት ኃይል ላለመስጠት መወሰኑ በሥነ-ሥርዓትም ሆነ በመሰረታዊ ህግ ይዘት ችግር የለውም፡፡ በወቅቱ ላልነበረ ሕግ አልተገበርክም ተብሎ ችሎቱን መተቸት የሚቻልበት የህግ አግባብ የለም፡፡ እንዲሁም የአዋጅ ቁጥር 1324/2016 የአንቀጽ 65(1)
የሽግግር ድንጋጌ ራሱ አዲሱ ሕግ በመታየት ላይ ባሉ ጉዳዮች ላይ እንደማይሠራ በማረጋገጥ ይህንን ያጠናክረዋል፡፡ ሆኖም ችሎቱ የሕግ ክፍተቱን ለመሙላት የመረጠው የአመሳስሎሽ ድልድይ፤ ማለትም ከአራተኛው መጽሐፍ (የግዴታዎች ሕግ) የተወሰደው የፍ/ብ/ሕ/ቁ 1845 የ10 ዓመት ይርጋ፣ የሕግ አውጪው ከጊዜ በኋላ በአዋጅ 1324/2016 አንቀጽ 64(2) ለገጠር መሬት ክስ የ15 ዓመት ይርጋን መደንገጉን ስናይ በፅንሰ-ሐሳብ (በዶክትሪን) ደረጃ የጎላ ክፍተት ያለበት ሆኖ ይታያል፡፡ የሕግ አውጪው የገጠር መሬት ይርጋን የ15 ዓመት የይዞታ (Adverse possession) ሥርዓት ከሚደነግገው የፍ/ብ/ሕ/ቁ 1168 ጋር ማጣመሩ፣ ለመሬት ማስለቀቅ ክሶች ተፈጥሯዊ እና ፅንሰ-ሐሳባዊ ወጥነት ያለው የአመሳስሎሽ ምንጭ የሚገኘው በንብረት ሕጉ ማዕቀፍ ውስጥ እንጂ በውል ግዴታዎች ማዕቀፍ ውስጥ አለመሆኑን የሚያስገነዝብ ሁኖ ይገኛል ችሎቱ ከፍ/ህ/ቁጥር 1168 ይልቅ አንቀጽ 1845 ድንጋጌን መምረጡ በፅሑፋዊ ትርጓሜ ሊደገፍ የሚችል ቢሆንም፣ በኢትዮጵያ የመሬት ሕግ ውስጥ ሁለት የተምታታ እና የሚጋጭ ሥርዓት (Dual and conflicting regime) ይዞ ብቅ ብሏል፡፡ ምንም እንኳን ሕገ-መንግሥታዊ መሠረታቸው እና የመብታቸው የሕግ ባህሪ አንድ ዓይነት ቢሆንም፣ የከተማ መሬት ክስ በ10 ዓመት፣ የገጠር መሬት ክስ ደግሞ በ15 ዓመት እንዲታገድ ማድረግ የህግ ባለሙያውንም ሆነ ሌላውን የማህበረሰብ ክፍል የሚያሳምን ሊሆን አይችልም፡፡
ይህ ሥርዓታዊ አለመጣጣም ከሁለት በአንዱ መንገድ ዕልባት እስካላገኘ ድረስ የኢትዮጵያን የንብረት ሕግ ስነ ህግ እድገና የአስገዳጅ ህግ ትርጉም ወጥነት ግብ በፅኑ መፈተኑን የሚይቀጥል መሆኑ ይገመታል፡፡ ስለሆነም ባለሰባት ዳኞች ሰበር ችሎት ለከተማ መሬት የሰጠውን አስገዳጅ ትርጉም ከፍ/ህ/ቁጥር 1168 መሰረተ ሃሳብና ከተገቢው የህግ አተረጓጎም ስልት አንፃር በድጋሚ በመገምገም በቅርብ ጊዜ በወጣው የገጠር መሬት ህግ ውስጥ ከተደነገገው የ15 ዓመት ማዕቀፍ ጋር ያጣጥመዋል፣ አለበለዚያ ደግሞ የሕግ አውጪው (ፓርላማው) ከገጠር መሬት ሥርዓት ጋር የተናበበ የይርጋ ድንጋጌን ያካተተ አጠቃላይ የከተማ መሬት አስተዳደር አዋጅ ያወጣል፡፡ ከፍ ሲል ደግሞ የፌዴሬሽን ምክር ቤት ከላይ ከተጠቀሰው ህገ መንግስቱ ጥበቃ አንፃር አይቶ ህገ መንግስታዊ ትርጉም ሊሰጠበት ይችላል፡፡ ይህ የእርምት እርምጃ እስኪወሰድ ድረስ ለአንድ ዓይነት ሕገ-መንግሥታዊ መብት፤ በከተማ 10 ዓመት፣ በገጠር 15 ዓመት ሊሆን ይገባል ተብሎ የተከፋፈለው የይርጋ ጊዜ በኢትዮጵያ የመሬት ሕግ እና በአስገዳጅ የህግ ትርጉም ስርዓት ላይ ያልተፈታ ፅንሰ-ሐሳባዊ መዛባት (Doctrinal anomaly) ሆኖ መቀጠሉ አይቀሬ ነው፡፡ በመሆኑም ይህ በችሎቱ ውሳኔ እንደድክመት ሊነሳ የሚችል ተገቢ ምልክታ ነው የሚል እምነት አለኝ፡፡
ክፍል ስምንት፡ አጠቃላይ ማጠቃለያ
የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የሰባት ዳኞች ሰበር ችሎት የሰጠው ይህ ውሳኔ ተቃርኖ ያለባቸውን አስገዳጅ የህግ ትርጉሞችን ከማረቅና የስርዓቱን ወጥነትና ተገማችነት ከማስፈን አንፃ እጅግ መሠረታዊ እና አስፈላጊ ቢሆንም በአገሪቱ የንብረት እና የመሬት ሕግ ስነ ህግ ላይ ህገ መንግስታዊ መሰረትን ባልተጎናፀፈ አመክንዮ ተመሳሳይ ጥበቃ ያለውን የባለይዞታነት መብት በተለያዩ የይርጋ ጊዜያት እንዲገዙ ስርዓት ያበጀ በመሆኑ አከራካሪነቱ አይቀሬ ይመስለኛል፡፡ ውሳኔው በቀድሞ አስገዳጅ ውሳኔዎች መካከል የነበረውን ጥልቅ ተቃርኖ ሕገ-መንግሥታዊ መሠረትን እና የፍትሐብሔር ሕግን አግባብነት ያላቸውን መርሆች በሚገባ በመመርመር ተገቢውን የዳኝነት ጥበብ በመጠቀም ለመፈታት የተቻለበት መሆኑ ይታመናል፡፡ በተለይም የባለቤትነት መብትን (Ownership) ከይዞታ መብት (Holding rights) በሚገባ በመለየት፣ ለባለቤትነት የተፈጠሩ የሕግ ማዕቀፎችን የግል የመሬት ባለቤትነት በማይፈቅድ ሕገ-መንግሥታዊ ሥርዓት ውስጥ በቀጥታ ተግባራዊ ማድረግ የማይቻል መሆኑን አሳይቷል፡፡ ይህ የሕግ ትርጉም በኢትዮጵያ የከተማ መሬት ይዞታ ክርክሮች ላይ ፅንሰ-ሐሳባዊ ጥራትን፣ ሥርዓታዊ ወጥነትን እና ተገማችነትን በማምጣት ወደፊት ለሚነሱ የንብረት ሕግ ክርክሮች ጠንካራ መሠረት የሚጥል አንፀባራቂ የዳኝነት አሻራ ነው ተብሎ ቢውሰድ ማጋነን አይሆንብኝም፡፡ ሆኖም ከላይ በክፍል 7 ስር በሰፊው እንደተብራራው ችሎቱ የሕግ ክፍተቱን ለመሙላት የመረጠው የአመሳስሎሽ ድልድይ፤ ማለትም ከአራተኛው መጽሐፍ (የግዴታዎች ሕግ) የተወሰደው የፍ/ብ/ሕ/ቁ 1845 የ10 ዓመት ይርጋ፣ የሕግ አውጪው ከጊዜ በኋላ በአዋጅ 1324/2016 አንቀጽ 64(2) ለገጠር መሬት ክስ የ15 ዓመት ይርጋን መደንገጉን ስናይ በፅንሰ-ሐሳብ (በዶክትሪን) ደረጃ የጎላ ክፍተት ያለበት ሆኖ ይታያል፡፡ ስለሆነም ችሎቱ በራሱ አነሳሽነት የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ወይስ የፌዴፌሬሽን ምክር ቤት? ትክክለኛውን መስመስር ይለዩ ይሆን? በዚህ ነጥብ ላይ ሁላችንንም ሊያስተምር የሚችል የምርምር ስራ ወይም የውሳኔ ትችት እይታ በዘርፉ በበቁ በአወቁ የአገራችን ምሁራን ሊከናወን እንደሚችል ተስፋ አደርጋለሁ፡፡
አበቃ!!
ተፃፈ በአልማው ወሌ
መጋቢት 04 ቀን 2018 ዓ/ም
አዲስ አበባ
ማስታወሻ፦ ፅሁፉ ጥብቅ የምርምር ዘዴ በመከተል ያልተከናወነ መሆኑን ከወዲሁ እየገለፅሁ ለወደፊቱ ግን በዚሁ አርዕስትና ተያያዥ የህግ ጉዳዮች ላይ ፈጣሪ አምላክ ፍቃዱ ከሆነ ሙያዊ እና አካዳሚያዊ ደረጃውን የጠበቀ ስራ ይዠ ለመቅረብ እሞክራለሁ፡፡ ማናቸውም ስህተቶች የራሴው መሆናቸው እንዲታወቅልኝም እፈልጋለሁ፡፡
https://www.facebook.com/s...
https://www.facebook.com/s...