13 hours ago
ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) የወልቂጤ መሶብ የአንድ ማዕከልን አገልግሎት ሥራ አስጀመሩ
**********************
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) በክልሉ ወልቂጤ ከተማ በክልሉ 3ኛውን መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫ በይፋ መርቀው አገልግሎት አስጀምረዋል።
የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በ7 ተቋማት 22 አገልግሎት እየተሰጠ መሆኑም ተገልጿል፡፡
የአገልግሎት አሰጣጥ ችግር ያለባቸው፣ ተገልጋይ የሚበዛባቸው፣ ለሙስናና ብልሹ አሠራር የተጋለጡ እንዲሁም ቅሬታ የሚበዛባቸው ተቋማት ተለይተው ወደ ማዕከሉ እንዲገቡ መደረጋቸው በወቅቱ ተጠቁሟል፡፡
የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ዜጎች በአንድ ቦታ ብዙ አገልግሎቶችን በቀላሉ እንዲያገኙ፣ ጊዜና ወጪ እንዲቆጥቡ እና የአገልግሎት ጥራት እንዲሻሻል የሚያስችል ዘመናዊ የአገልግሎት ሥርዓት መሆኑ ተመላክቷል፡፡
በማስጀመሪያ መርሐ ግብሩ የክልሉ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ወይዘሮ ፋጤ ስርሞሎን ጨምሮ የተለያዩ የክልልና ዞን መንግሥት ስራ ኃላፊዎች መገኘታውን የክልሉ ኮሙኒኬሽን ቢሮ መረጃ ያመላክታል፡፡
#ethiopia #ebc #ebcdotstream #mesob #onestopservice
**********************
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) በክልሉ ወልቂጤ ከተማ በክልሉ 3ኛውን መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫ በይፋ መርቀው አገልግሎት አስጀምረዋል።
የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በ7 ተቋማት 22 አገልግሎት እየተሰጠ መሆኑም ተገልጿል፡፡
የአገልግሎት አሰጣጥ ችግር ያለባቸው፣ ተገልጋይ የሚበዛባቸው፣ ለሙስናና ብልሹ አሠራር የተጋለጡ እንዲሁም ቅሬታ የሚበዛባቸው ተቋማት ተለይተው ወደ ማዕከሉ እንዲገቡ መደረጋቸው በወቅቱ ተጠቁሟል፡፡
የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ዜጎች በአንድ ቦታ ብዙ አገልግሎቶችን በቀላሉ እንዲያገኙ፣ ጊዜና ወጪ እንዲቆጥቡ እና የአገልግሎት ጥራት እንዲሻሻል የሚያስችል ዘመናዊ የአገልግሎት ሥርዓት መሆኑ ተመላክቷል፡፡
በማስጀመሪያ መርሐ ግብሩ የክልሉ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ወይዘሮ ፋጤ ስርሞሎን ጨምሮ የተለያዩ የክልልና ዞን መንግሥት ስራ ኃላፊዎች መገኘታውን የክልሉ ኮሙኒኬሽን ቢሮ መረጃ ያመላክታል፡፡
#ethiopia #ebc #ebcdotstream #mesob #onestopservice
13 hours ago
የወልቂጤ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ተመረቀ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 8፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) በወልቂጤ ከተማ የክልሉን 3ኛ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መርቀው ሥራ አስጀምረዋል፡፡
መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ዜጎች በአንድ ቦታ ብዙ አገልግሎቶችን በቀላሉ እንዲያገኙ፣ ጊዜና ወጪ እንዲቆጥቡና የአገልግሎት ጥራት እንዲሻሻል የሚያስችል ሥርዓት ነው።
በተቀናጀ መረጃ አሰጣጥ የዜጎችን እርካታ በማሳደግና የመንግሥት ተቋማት ቅንጅታዊ አሰራርን በማጎልበት ረገድ ከፍተኛ ሚና እንዳለውም ተመላክቷል፡፡
የወልቂጤ የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በውስጡ 6 ተቋማት የያዘ ሲሆን÷ በአጠቃላይ 42 የተለያዩ አገልግሎቶችን እንደሚሰጥ የክልሉ ኮሙኒኬሽን ለፋና ዲጂታል ገልጿል፡፡
ከፍተኛ የአገልግሎት አሰጣጥ ችግር ያለባቸው፣ ተገልጋይ የሚበዛባቸው፣ ለሙስናና ብልሹ አሠራር የተጋለጡ እንዲሁም ቅሬታ የሚበዛባቸው ተቋማት ተለይተው ወደ ማዕከሉ እንዲገቡ ተደርጓል።
ተቋማትን ከወረቀት ንክኪ ነጻ እና በውጤት ወደሚለካ አሠራር ለማሸጋገር እየተተገበሩ ካሉ የለውጥ ሥራዎች መካከል "የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት" ተጠቃሽ ነው፡፡
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 8፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) በወልቂጤ ከተማ የክልሉን 3ኛ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መርቀው ሥራ አስጀምረዋል፡፡
መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ዜጎች በአንድ ቦታ ብዙ አገልግሎቶችን በቀላሉ እንዲያገኙ፣ ጊዜና ወጪ እንዲቆጥቡና የአገልግሎት ጥራት እንዲሻሻል የሚያስችል ሥርዓት ነው።
በተቀናጀ መረጃ አሰጣጥ የዜጎችን እርካታ በማሳደግና የመንግሥት ተቋማት ቅንጅታዊ አሰራርን በማጎልበት ረገድ ከፍተኛ ሚና እንዳለውም ተመላክቷል፡፡
የወልቂጤ የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በውስጡ 6 ተቋማት የያዘ ሲሆን÷ በአጠቃላይ 42 የተለያዩ አገልግሎቶችን እንደሚሰጥ የክልሉ ኮሙኒኬሽን ለፋና ዲጂታል ገልጿል፡፡
ከፍተኛ የአገልግሎት አሰጣጥ ችግር ያለባቸው፣ ተገልጋይ የሚበዛባቸው፣ ለሙስናና ብልሹ አሠራር የተጋለጡ እንዲሁም ቅሬታ የሚበዛባቸው ተቋማት ተለይተው ወደ ማዕከሉ እንዲገቡ ተደርጓል።
ተቋማትን ከወረቀት ንክኪ ነጻ እና በውጤት ወደሚለካ አሠራር ለማሸጋገር እየተተገበሩ ካሉ የለውጥ ሥራዎች መካከል "የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት" ተጠቃሽ ነው፡፡
2 days ago
እባካችሁ በኦቲዝም ስም አትነግዱ!
"ከወላጆች አይን እንባ በዝታለች፣ እግዚአብሄርም ያያል !"
( መላኩ ብርሃኑ)
ኢትዮጵያ ውስጥ ኦቲዝም "እጅግ በጣም ውድ" ችግር ነው፡፡ ከኦቲዝም ጋር በተያያዘ የወላጅን ሸክም ለማቅለል የተዘረጋ ምንም አይነት ስርዓት ስለሌለ ኦቲዝም ወደአንድ ቤት ሲመጣ የዚያ ቤት ህይወት ከመሰረቱ ይናጋል።
ልጆቹ የሙሉ ጊዜ ጥበቃ ስለሚያስፈልጋቸው ወላጅ እየሰራ ከሆነ ስራውን፣ እየተማረ ከሆነም ትምህርቱን ለመተው ይገደዳል። ይህ ደግሞ ለኦኮኖሚ ጫና፣ ለስነልቡና ቀውስ፣ ለማህበራዊ ግንኙነት መዳከምና አልፎ ተርፎም ለከባድ የጤና ቀውስ ይዳርጋል።
እስኪ አስቡት !
ኢትዮጵያ ውስጥ አንድ ልጅ ኦቲዝም እንዳለበት ለመመርመር (Diagnose) ለማድረግ የላብሯቶሪ ወጪውን ሳይጨምር ለህክምና ባለሙያው ብቻ የሚከፈል እስከ 20 ሺህ ብርና ከዚያ በላይ ይደርሳል።
እስከ 25 ሺህ ብር የሚደርስ የሃገር ውስጥ ምርመራን እንተወውና እንደ yeast overgrowth, heavy metal test, OAT test, FRAT test ውጪ ልኮ ለማሰራት ከ100 -200 ሺህ ብር በላይ ይጠየቃል።
ኦቲዝም ያላቸው ልጆች ብዙውን ጊዜ ከአንጀታቸው ጋር የተያያዘ የጤና ችግር አለባቸው ተብሎ ስለሚታመን 'ግሉቲን እና ኬዚን' የሚባሉ ንጥረነገሮች ካሏቸው ምግቦች ነጻ መሆን አለባቸው። እኛ ሃገር ደግሞ “ግሉቲን ፍሪ፣ ኬዚን ፍሪ” የሚባሉት የምግብ አይነቶች በአቅርቦት ደረጃ ውስንና በጣም ውድ ናቸው።ከሰንዴ ዘርና ከወተት መራቅ አለባቸው።
ለነሱ የሚሆን ወተት ለመስራት የሚጠቅም አንድ ኪሎ 'አልመንድ' የሚባል ፍሬ በትንሹ እስከ 5 ሺህ ብር ያስወጣል። ምግባቸው ውድ በሆነው የንጹህ የወይራ ዘይት ካልሆነ በቀር በሌላ መሰራት አይችልም። ስኳርና ሰውሰራሽ ማጣፈጫ ስለማይጠቀሙ በምትኩ ቴምር ለመግዛት በኪሎ ከ1500-3500 ብር ድረስ ይጠይቃል።
በዚህ ሳቢያ ልጆቹ የሚወስዱት ምግብ አይነት ስለሚያንስ እንዳይጎዱ ሲባል 'ሰፕሊመንት' ያስፈልጋቸዋል። ለምሳሌ ለነሱ የሚሆን የአሳ ዘይት ዋጋው ከ 12 ሺህ እስከ 35ሺህ ብር ይሸጣል። ለጥቂት ቀን ብቻ የሚሆን ቫይታሚን ዲ ደግሞ እስከ 5 ሺህ ብር ይሸጣል። አቅም ላለው ወላጅ እንኳን ሌሎች ሌሎች ተጨምረው የሰፕሊመንት ዋጋ ብቻ በወር ከ50 ሺህ ብር በላይ ያስወጣዋል።
በአጠቃላይ ለአንድ ኦቲዝም ላለበት ልጅ የሚወጣው የአንድ ወር የምግብ ወጪ አንድ ቤት ውስጥ ለሙሉ ቤተሰብ ከሚወጣው የቀለብ ወጪ ይበልጣል።
ኦቲዝም በሽታ ስላልሆነ መድሃኒት የለውም፡፡ ለኦቲዝም የሚደረገው ድጋፍ በአብዛኛው የንግግር፣ የባህሪና የአካልና ሰውነት ቅንጅት ቴራፒ ነው፡፡ እዚህ ጋር ደግሞ ነጋዴዎቹ ተሰብስበዋል።
የሚችሉትም የማይችሉትም የሆነች ዛኒጋባ ተከራይተው እንሰጣለን ለሚሉት ተራፒ የሚያስከፍሉት ዋጋ በጣም ውድ ነው። ለአንድ ልጅ በወር 30 ሰዓት ቴራፒ ለመስጠት የሚከፈለው ገንዘብ የአንድ ልጅን የ6 ወር የግል ትምህርት ቤት ክፍያ ይበልጣል።
በቁጥር ጥቂት የሆኑት 'የልዩ ፍላጎት አካቶ' ያላቸው ትምህርት ቤቶች ክፍያ ዋጋ ደግሞ አይወራ። ታዋቂ ነን የሚሉት አንዳንዶቹ ትምህርት ቤቶች በወር እስከ 100 ሺህ ብር ያስከፍላሉ። በጨበጣ ያለምንም እውቀት ኦቲዝምን ቢዝነስ ያደረጉ አንዳንድ ነጋዴ ግለሰቦች የከፈቱት ትምህርት ቤት ደሞ አለ። አዳሪ ብለው እስከ 300ሺህ ብር በወር ያስከፍላሉ።
ኢንተርናሽናል ትምህርት ቤቶች እንኳን የማያስከፍሉትን አይነት ገንዘብ የሚያስከፍሉ አካቶ ት/ቤቶችና በኦቲዝም ስም የተቋቋሙ ተቋማት በጣም ብዙ ናቸው፡፡
በዚህ ላይ ልጁ ትምህርት ቤት ሲሄድም ሆነ ሲመለስ ሰርቪስ የሚጠቀም ከሆነ ወላጆች ለመጓጓዣው ከመደበኞቹ ህጻናት በእጥፍ እንዲከፍሉ ይደረጋሉ፡፡
ይህን ይህን ሳይ በሃገሬ ተስፋ እቆርጣለሁ። ስርዓት ያልተዘረጋለት፣ ደንብና ህግ ያልወጣለት፣ በሙስና ሰንሰለት የተጨማለቀ ፣ ከኤንጂኦ እስከ ግለሰቦች ድረስ በኦቲዝም ስም የጦፈ ንግድ ሲካሄድ ሃይ ባይ የታጣበት ሃገር ላይ ነን ያለነው።
እንደኔ ጠለቅ ብሎ ለሚያየው እዚህ ዘርፍ ላይ ያለው መጨመላለቅና ብዝበዛ በጣም ይሰቀጥጣል፡፡
መቼም በጥቂቱ ካነሳሁት እውነት አንጻር በዚህ ዘመን የኑሮ ውድነት አንድ ወላጅ ቤት ኦቲዝም ሲደረብበት በስነልቡናም፣ በገንዘብም ምን ያህል ከባድ የህይወት መርግ እንደሚፈጥር ካሰባችሁት ይበቃል፡፡
እናንት 'ሞራል አልባ' ነጋዴዎች! እንዲህ ባለ 'ውድ' ችግር ላይ አይናችሁን አጥባችሁ ገንዘብ ለማጋበስና መሄጃ አጥቶ የተቸገረውን ወላጅ ለመበዝበዝ እንዴት ህሊናችሁ እሺ አላችሁ ግን? (በርግጥ ህሊና የላችሁም!)
በጣም ነው የሚያሳዝነው፡፡ይህ'ኮ ኢሰብአዊነት ነው። ወንጀል ነው። የሞራል ዝቅጠት ነው። ዛሬ ከኔ ባልተሻለ ጥቂት ንባብ ብቻ ተነስታችሁ ቤት ተከራይታችሁና ማዕከል ከፍታችሁ ‘ባለሙያ ነን’ እያላችሁ 'ቢዝነስ' የምትሰሩ ፣ ቲክቶኩንና ሶሻል ሚዲያውን ያጣበባችሁ ሰዎች ... ምናችሁን ነው የሚያማችሁ? ነገ'ኮ ይህ በህጋዊነት ሽፋን ያለቁጥጥር በተለቀቀ ሜዳ ላይ ስትፋንኑ የበደላችሁት ወላጅ እንባ ቤታችሁ ድረስ ይመጣል።
ኦቲዝም ላይ እንሰራለን ብላችሁ የምትደሰኩሩ ሃኪሞችምም፣ ሳይኮሎጂስቶችም፣ ቴራፒስቶችም፣ አካቶ ትምህርት ቤቶችም፣ማዕከላትም ቆም ብላችሁ ብታስቡ ይበጃችኋል!
ይህ ምርጫ ያጣ… ተመልካች ያጣ፣ ልጄ ቢሻሻልልኝ ብሎ እዚህም እዚያም መፍትሄ ፍለጋ የሚኳትን ወላጅ በኦቲዝም ምክንያት ጥሪቱን አሟጦ ሌሎች ልጆቹን የሚያሳድግበትና ቤቱን የሚመራበት ገንዘብ እስኪያጣ ድረስ ሲቸገር እናንተ አላግባብ በዘረፋችሁት ገንዘብ ሰላም፣ ጤናና የሰላም እንጀራ አይኖራችሁም ።
አያሳዝናችሁም ግን ? በናንተ የዋጋ ውድነትና ሳቢያ አቅም አጥቶ ዕድሜውን ሙሉ ‘ለልጄ ይህንን ሳላደርግለት’ ብሎ በጸጸት እንባ የሚታጠብ ወላጅ ግን አያሳዝናችሁም?
በዚህ ወላጅ ላይ ህይወት ላይ እየተጫወታችሁ እስከመቼ ራሳችሁን ታበለጽጋላችሁ ?
አንድ ቀን ግን ይመጣል! አላግባብ ለምትሰበስቡት ትርፍ አንድ ቀን እግዚአብሄር ይፈርድባችኋል ! የወላጅ እንባ በቤታችሁና በልጆቻችሁ ላይ ይመጣል። ያኔ እናንተም ቁጭ ብላችሁ ታለቅሳላችሁ !
(ማሳሰቢያ ፤ ይህ ጽሁፍ በሃቅ የሚሰሩ፣ ልጆቹንና ወላጆችን ለመርዳት የሚለፉትን ባለሙያዎች አይመለከትም)
ሜርድ!!
"ከወላጆች አይን እንባ በዝታለች፣ እግዚአብሄርም ያያል !"
( መላኩ ብርሃኑ)
ኢትዮጵያ ውስጥ ኦቲዝም "እጅግ በጣም ውድ" ችግር ነው፡፡ ከኦቲዝም ጋር በተያያዘ የወላጅን ሸክም ለማቅለል የተዘረጋ ምንም አይነት ስርዓት ስለሌለ ኦቲዝም ወደአንድ ቤት ሲመጣ የዚያ ቤት ህይወት ከመሰረቱ ይናጋል።
ልጆቹ የሙሉ ጊዜ ጥበቃ ስለሚያስፈልጋቸው ወላጅ እየሰራ ከሆነ ስራውን፣ እየተማረ ከሆነም ትምህርቱን ለመተው ይገደዳል። ይህ ደግሞ ለኦኮኖሚ ጫና፣ ለስነልቡና ቀውስ፣ ለማህበራዊ ግንኙነት መዳከምና አልፎ ተርፎም ለከባድ የጤና ቀውስ ይዳርጋል።
እስኪ አስቡት !
ኢትዮጵያ ውስጥ አንድ ልጅ ኦቲዝም እንዳለበት ለመመርመር (Diagnose) ለማድረግ የላብሯቶሪ ወጪውን ሳይጨምር ለህክምና ባለሙያው ብቻ የሚከፈል እስከ 20 ሺህ ብርና ከዚያ በላይ ይደርሳል።
እስከ 25 ሺህ ብር የሚደርስ የሃገር ውስጥ ምርመራን እንተወውና እንደ yeast overgrowth, heavy metal test, OAT test, FRAT test ውጪ ልኮ ለማሰራት ከ100 -200 ሺህ ብር በላይ ይጠየቃል።
ኦቲዝም ያላቸው ልጆች ብዙውን ጊዜ ከአንጀታቸው ጋር የተያያዘ የጤና ችግር አለባቸው ተብሎ ስለሚታመን 'ግሉቲን እና ኬዚን' የሚባሉ ንጥረነገሮች ካሏቸው ምግቦች ነጻ መሆን አለባቸው። እኛ ሃገር ደግሞ “ግሉቲን ፍሪ፣ ኬዚን ፍሪ” የሚባሉት የምግብ አይነቶች በአቅርቦት ደረጃ ውስንና በጣም ውድ ናቸው።ከሰንዴ ዘርና ከወተት መራቅ አለባቸው።
ለነሱ የሚሆን ወተት ለመስራት የሚጠቅም አንድ ኪሎ 'አልመንድ' የሚባል ፍሬ በትንሹ እስከ 5 ሺህ ብር ያስወጣል። ምግባቸው ውድ በሆነው የንጹህ የወይራ ዘይት ካልሆነ በቀር በሌላ መሰራት አይችልም። ስኳርና ሰውሰራሽ ማጣፈጫ ስለማይጠቀሙ በምትኩ ቴምር ለመግዛት በኪሎ ከ1500-3500 ብር ድረስ ይጠይቃል።
በዚህ ሳቢያ ልጆቹ የሚወስዱት ምግብ አይነት ስለሚያንስ እንዳይጎዱ ሲባል 'ሰፕሊመንት' ያስፈልጋቸዋል። ለምሳሌ ለነሱ የሚሆን የአሳ ዘይት ዋጋው ከ 12 ሺህ እስከ 35ሺህ ብር ይሸጣል። ለጥቂት ቀን ብቻ የሚሆን ቫይታሚን ዲ ደግሞ እስከ 5 ሺህ ብር ይሸጣል። አቅም ላለው ወላጅ እንኳን ሌሎች ሌሎች ተጨምረው የሰፕሊመንት ዋጋ ብቻ በወር ከ50 ሺህ ብር በላይ ያስወጣዋል።
በአጠቃላይ ለአንድ ኦቲዝም ላለበት ልጅ የሚወጣው የአንድ ወር የምግብ ወጪ አንድ ቤት ውስጥ ለሙሉ ቤተሰብ ከሚወጣው የቀለብ ወጪ ይበልጣል።
ኦቲዝም በሽታ ስላልሆነ መድሃኒት የለውም፡፡ ለኦቲዝም የሚደረገው ድጋፍ በአብዛኛው የንግግር፣ የባህሪና የአካልና ሰውነት ቅንጅት ቴራፒ ነው፡፡ እዚህ ጋር ደግሞ ነጋዴዎቹ ተሰብስበዋል።
የሚችሉትም የማይችሉትም የሆነች ዛኒጋባ ተከራይተው እንሰጣለን ለሚሉት ተራፒ የሚያስከፍሉት ዋጋ በጣም ውድ ነው። ለአንድ ልጅ በወር 30 ሰዓት ቴራፒ ለመስጠት የሚከፈለው ገንዘብ የአንድ ልጅን የ6 ወር የግል ትምህርት ቤት ክፍያ ይበልጣል።
በቁጥር ጥቂት የሆኑት 'የልዩ ፍላጎት አካቶ' ያላቸው ትምህርት ቤቶች ክፍያ ዋጋ ደግሞ አይወራ። ታዋቂ ነን የሚሉት አንዳንዶቹ ትምህርት ቤቶች በወር እስከ 100 ሺህ ብር ያስከፍላሉ። በጨበጣ ያለምንም እውቀት ኦቲዝምን ቢዝነስ ያደረጉ አንዳንድ ነጋዴ ግለሰቦች የከፈቱት ትምህርት ቤት ደሞ አለ። አዳሪ ብለው እስከ 300ሺህ ብር በወር ያስከፍላሉ።
ኢንተርናሽናል ትምህርት ቤቶች እንኳን የማያስከፍሉትን አይነት ገንዘብ የሚያስከፍሉ አካቶ ት/ቤቶችና በኦቲዝም ስም የተቋቋሙ ተቋማት በጣም ብዙ ናቸው፡፡
በዚህ ላይ ልጁ ትምህርት ቤት ሲሄድም ሆነ ሲመለስ ሰርቪስ የሚጠቀም ከሆነ ወላጆች ለመጓጓዣው ከመደበኞቹ ህጻናት በእጥፍ እንዲከፍሉ ይደረጋሉ፡፡
ይህን ይህን ሳይ በሃገሬ ተስፋ እቆርጣለሁ። ስርዓት ያልተዘረጋለት፣ ደንብና ህግ ያልወጣለት፣ በሙስና ሰንሰለት የተጨማለቀ ፣ ከኤንጂኦ እስከ ግለሰቦች ድረስ በኦቲዝም ስም የጦፈ ንግድ ሲካሄድ ሃይ ባይ የታጣበት ሃገር ላይ ነን ያለነው።
እንደኔ ጠለቅ ብሎ ለሚያየው እዚህ ዘርፍ ላይ ያለው መጨመላለቅና ብዝበዛ በጣም ይሰቀጥጣል፡፡
መቼም በጥቂቱ ካነሳሁት እውነት አንጻር በዚህ ዘመን የኑሮ ውድነት አንድ ወላጅ ቤት ኦቲዝም ሲደረብበት በስነልቡናም፣ በገንዘብም ምን ያህል ከባድ የህይወት መርግ እንደሚፈጥር ካሰባችሁት ይበቃል፡፡
እናንት 'ሞራል አልባ' ነጋዴዎች! እንዲህ ባለ 'ውድ' ችግር ላይ አይናችሁን አጥባችሁ ገንዘብ ለማጋበስና መሄጃ አጥቶ የተቸገረውን ወላጅ ለመበዝበዝ እንዴት ህሊናችሁ እሺ አላችሁ ግን? (በርግጥ ህሊና የላችሁም!)
በጣም ነው የሚያሳዝነው፡፡ይህ'ኮ ኢሰብአዊነት ነው። ወንጀል ነው። የሞራል ዝቅጠት ነው። ዛሬ ከኔ ባልተሻለ ጥቂት ንባብ ብቻ ተነስታችሁ ቤት ተከራይታችሁና ማዕከል ከፍታችሁ ‘ባለሙያ ነን’ እያላችሁ 'ቢዝነስ' የምትሰሩ ፣ ቲክቶኩንና ሶሻል ሚዲያውን ያጣበባችሁ ሰዎች ... ምናችሁን ነው የሚያማችሁ? ነገ'ኮ ይህ በህጋዊነት ሽፋን ያለቁጥጥር በተለቀቀ ሜዳ ላይ ስትፋንኑ የበደላችሁት ወላጅ እንባ ቤታችሁ ድረስ ይመጣል።
ኦቲዝም ላይ እንሰራለን ብላችሁ የምትደሰኩሩ ሃኪሞችምም፣ ሳይኮሎጂስቶችም፣ ቴራፒስቶችም፣ አካቶ ትምህርት ቤቶችም፣ማዕከላትም ቆም ብላችሁ ብታስቡ ይበጃችኋል!
ይህ ምርጫ ያጣ… ተመልካች ያጣ፣ ልጄ ቢሻሻልልኝ ብሎ እዚህም እዚያም መፍትሄ ፍለጋ የሚኳትን ወላጅ በኦቲዝም ምክንያት ጥሪቱን አሟጦ ሌሎች ልጆቹን የሚያሳድግበትና ቤቱን የሚመራበት ገንዘብ እስኪያጣ ድረስ ሲቸገር እናንተ አላግባብ በዘረፋችሁት ገንዘብ ሰላም፣ ጤናና የሰላም እንጀራ አይኖራችሁም ።
አያሳዝናችሁም ግን ? በናንተ የዋጋ ውድነትና ሳቢያ አቅም አጥቶ ዕድሜውን ሙሉ ‘ለልጄ ይህንን ሳላደርግለት’ ብሎ በጸጸት እንባ የሚታጠብ ወላጅ ግን አያሳዝናችሁም?
በዚህ ወላጅ ላይ ህይወት ላይ እየተጫወታችሁ እስከመቼ ራሳችሁን ታበለጽጋላችሁ ?
አንድ ቀን ግን ይመጣል! አላግባብ ለምትሰበስቡት ትርፍ አንድ ቀን እግዚአብሄር ይፈርድባችኋል ! የወላጅ እንባ በቤታችሁና በልጆቻችሁ ላይ ይመጣል። ያኔ እናንተም ቁጭ ብላችሁ ታለቅሳላችሁ !
(ማሳሰቢያ ፤ ይህ ጽሁፍ በሃቅ የሚሰሩ፣ ልጆቹንና ወላጆችን ለመርዳት የሚለፉትን ባለሙያዎች አይመለከትም)
ሜርድ!!
3 days ago
ኮካ ኮላ ኩባንያ የአለም ዋንጫን የመክፈቻ ስነስርአት በአዲስ አበባ በደመቀ ሁኔታ አከናወነ፡፡ የአለም ዋንጫ የረጅም ጊዜ አጋርና ዋና ስፖንሰር የሆነው ኮካ ኮላ ኩባንያ በመላው አለም የአለም ዋንጫ መክፈቻ ስነስርአትን በደመቀ ሁኔታ እንዲከናወን አድርጓል፡፡ ከእነዚህ ስነስርአቶች መካከል በአዲስ አበባ ከተማ ስካይ ላይት ሆቴል የተደረገው ዝግጅት አንዱ ነው፡፡ ትላንት ምሽት በተከናወነው በዚህ ዝግጅት በርካታ ታዋቂ ሰዎች፣ የኪነጥበብ ባለሙያዎች፣ የስፖርት ቤተሰቦችና ጋዜጠኞች የታደሙ ሲሆን ጋዜጠኛ ሰኢድ ኪያር ዝግጅቱን መርቶታል፡፡ በፕሮግራሙ ላይ የኮካ ኮላ ሲኒየር ማርኬቲንግ ማኔጀር ሜሮን ብርሀኑ ሲናገሩ ‹‹እግር ኳስ ከስፖርትነቱ ባለፈ ሰዎችን በስሜትና በፍቅር የሚያስተሳስር ሁለተንተናዊ ቋንቋ ነው›› ብለዋል፡፡ የ2026ቱ አለም ዋንጫ በታሪክ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው አገራትና ጨዋታዎች የሚስተናገዱበት መሆኑን ጠቁመውም፣ ኮካ ኮላ ትርጉም ባላቸው አቀራረቦች የኢትዮጵያን እግር ኳስ አፍቃሪዎች ከውድድሩ ደስታ ጋር ይበልጥ ለማቀራረብ ቁርጠኛ መሆኑን ገልፀዋል፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ የኮካኮላ ቢቨሬጅስ ተወካይ በበኩላቸው ኩባንያ በኢትዮጵያ ውስጥ ስላለው ጠንካራ ተሳትፎና ምርት ስርጭት ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡ በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ ውስጥ በአዲስ አበባ፣ ሰበታ፣ ባህር ዳርና ድሬደዋን ጨምሮ 5 ፋብሪካዎች እንዳሉት ጠቅሰውም በተለያየ መጠን በብርጭቶ ጠርሙስና በፕላስቲክ ማሸጊያዎች ምርቶቹን እያቀረበ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ኮካ ኮላ እ.ኤ.አ ከ1978 አንስቶ የፊፋ አለም ዋንጫ ይፋዊ ስፖንሰር መሆኑ የሚታወቅ ነው፡፡
3 days ago
የጥገና ሥራ ለማከናወን የሚቋረጥ የኃይል አቅርቦት
ነገ ሰኔ 06 ቀን 2018 ዓ.ም የጥገና ሥራ ለማከናወን ኃይል የሚቋረጥባቸው አካባቢዎች፦
✅ ከጠዋቱ 2፡00 – 9፡30
አዲስ አበባና ሸገር
👉አፍንጮ በር መስጊድ፣ ደጃች ውቤ፣ ጊዮርጊስ እሳት አደጋ፣ ችሎት አደባባይ፣ ዘበኛ ሰፈር፣ ሾላ ፣ ኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት፣ ሰሜን ሆቴል ጫፍ ፣ቀለመወርቅ ት/ቤት፣ ዶሮ ተራ፣ ራስ ደስታ እና አካባቢቸው፣
👉 አርበኞች ት/ቤት፣ ዕንቁላል ፋብሪካ አደባባይ፣ ጎፋ ገብርኤል ከፍ ብሎ ቀበሌ 43 መዝናኛ፣ አልማዝዬ ሜዳ ፣ ሶፍያ ሞል አካባቢ፣ ሐመልማል ቤት አካባቢ፣ ቄራ በረት፣ ጎፋ ገብርኤል፣ ጎፋ ፖሊስ ጣቢያ እና አካባቢቸው፣
👉 ወይብላ ማርያም፣ አውጉስታ፣ አንፎ፣ ወይራ ሰፈር፣ ወይራ ኮንዶሚኒየም፣ ሞቢል ፣ ራሺያ ካምፕ፣ ተዘንአ ሆስፒታል፣ ሙስና ሰፈር፣ ቀራኒዮ አካባቢ፣ ሳሚ ካፌ፣ ታቦት ማደሪያ፣ 3 ቁጥር ማዞሪያ፣ ስላሴ ቤተክርስቲያን እና አካባቢቸው፣
👉 አየር ጤና፣ ናትራን፣ ለማ ነገዎ ሰፈር፣ አየር ጤና ሞቢል ጋዝ፣ ግራር ኮንዶሚኒየም፣ ረጲ ሳሙና ፋብሪካ፣ አጊማስ፣ 10 ኪሎ በከፊል፣ ዶሮ እርባታ፣ ቀንብሬ፣ አፍሪካ ልህቀት ማዕከል፣ አትሌቶች መንደር፣ ሚዛን ሹፉኔ፣ ኮካ ሰብስቴሽን አካባቢ፣ ሱሉልታ በከፊል፣ አካኮ እና አካባቢቸው፣
👉 አቃቂ ቄራ፣ 6 ወፍጮ፣ ንግድ ባንክ አካባቢ፣ መንህስት ት/ቤት አካባቢ፣ ተኩሼ እንጨት ቤት፣ መድኃኒዓለም ቤተክርስትያን አካባቢ፣ስ ልጤ ሰፈር መውጫ፣ ፋኑኤል ቤ/ክ፣ አጃንባ ኮንዶሚኒየም እና አካባቢቸው፣
👉 ነጋ ቦንገር ዝቅ ብሎ ፣ ጀሶ ፋብሪካ ፣ ብሔረ ፅጌ ቆዳ ፋብሪካ እና አካባቢው፣ ፓስታና መኮረኒ እና አካባቢው፣ ቀይ አፈር ባጃጅ ተራ አካባቢ፣ ጀሞ-1 ኮንዶሚኒየም፣ ለቡ መድኃኒዓለም፣ ጀሞ ሞል፣ ለቡ ሙዚቃ ሰፈር እና አካባቢቸው፣
✅ ከጠዋቱ 2፡00 – 12፡00
👉 መቀሌ - አብርሃ ካስትል፣ ቀበሌ 18፣ ዲያስፖራ፣ ማጂክ ስኩል፣ ደብረዳሞ፣ ሰማዕታት ሀውልት፣ ዲደብሊው ቢሮ፣ ፕላኔት ሆቴል፣ ጅብሩክ፣ እንደማርያም ጉግሳ አካባቢ፣ መቀሌ ሆስፒታል፣ ቀበሌ 14፣15፣16ና 17፣ አይናለም አካባቢ
✅ ከጠዋቱ 12፡00 – 6፡43
👉ሽሬ - ክሳደገባ፣ እንዳባጉና፣ ዛና፣ ምይሃንሴ፣ ደደቢት፣ ማይሊ፣ ሽራሮ፣ አዲሀገረይ፣ አዲነብሬድ፣ አዲዳእሮ፣ ማይፀብሪ፣ አዲአርካይ፣ አዲገብሩ እና አካባያቸው ላይ ኃይል ይቋረጣል።
ስለሆነም በተጠቀሱት አካባቢዎች የምትገኙ የተከበራችሁ ደንበኞቻችን የጥገና ሥራው ተጠናቆ የኃይል አቅርቦቱ እስኪመለስ ድረስ በትዕግስት እንድትጠብቁን እንጠይቃለን፡፡
#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት
ነገ ሰኔ 06 ቀን 2018 ዓ.ም የጥገና ሥራ ለማከናወን ኃይል የሚቋረጥባቸው አካባቢዎች፦
✅ ከጠዋቱ 2፡00 – 9፡30
አዲስ አበባና ሸገር
👉አፍንጮ በር መስጊድ፣ ደጃች ውቤ፣ ጊዮርጊስ እሳት አደጋ፣ ችሎት አደባባይ፣ ዘበኛ ሰፈር፣ ሾላ ፣ ኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት፣ ሰሜን ሆቴል ጫፍ ፣ቀለመወርቅ ት/ቤት፣ ዶሮ ተራ፣ ራስ ደስታ እና አካባቢቸው፣
👉 አርበኞች ት/ቤት፣ ዕንቁላል ፋብሪካ አደባባይ፣ ጎፋ ገብርኤል ከፍ ብሎ ቀበሌ 43 መዝናኛ፣ አልማዝዬ ሜዳ ፣ ሶፍያ ሞል አካባቢ፣ ሐመልማል ቤት አካባቢ፣ ቄራ በረት፣ ጎፋ ገብርኤል፣ ጎፋ ፖሊስ ጣቢያ እና አካባቢቸው፣
👉 ወይብላ ማርያም፣ አውጉስታ፣ አንፎ፣ ወይራ ሰፈር፣ ወይራ ኮንዶሚኒየም፣ ሞቢል ፣ ራሺያ ካምፕ፣ ተዘንአ ሆስፒታል፣ ሙስና ሰፈር፣ ቀራኒዮ አካባቢ፣ ሳሚ ካፌ፣ ታቦት ማደሪያ፣ 3 ቁጥር ማዞሪያ፣ ስላሴ ቤተክርስቲያን እና አካባቢቸው፣
👉 አየር ጤና፣ ናትራን፣ ለማ ነገዎ ሰፈር፣ አየር ጤና ሞቢል ጋዝ፣ ግራር ኮንዶሚኒየም፣ ረጲ ሳሙና ፋብሪካ፣ አጊማስ፣ 10 ኪሎ በከፊል፣ ዶሮ እርባታ፣ ቀንብሬ፣ አፍሪካ ልህቀት ማዕከል፣ አትሌቶች መንደር፣ ሚዛን ሹፉኔ፣ ኮካ ሰብስቴሽን አካባቢ፣ ሱሉልታ በከፊል፣ አካኮ እና አካባቢቸው፣
👉 አቃቂ ቄራ፣ 6 ወፍጮ፣ ንግድ ባንክ አካባቢ፣ መንህስት ት/ቤት አካባቢ፣ ተኩሼ እንጨት ቤት፣ መድኃኒዓለም ቤተክርስትያን አካባቢ፣ስ ልጤ ሰፈር መውጫ፣ ፋኑኤል ቤ/ክ፣ አጃንባ ኮንዶሚኒየም እና አካባቢቸው፣
👉 ነጋ ቦንገር ዝቅ ብሎ ፣ ጀሶ ፋብሪካ ፣ ብሔረ ፅጌ ቆዳ ፋብሪካ እና አካባቢው፣ ፓስታና መኮረኒ እና አካባቢው፣ ቀይ አፈር ባጃጅ ተራ አካባቢ፣ ጀሞ-1 ኮንዶሚኒየም፣ ለቡ መድኃኒዓለም፣ ጀሞ ሞል፣ ለቡ ሙዚቃ ሰፈር እና አካባቢቸው፣
✅ ከጠዋቱ 2፡00 – 12፡00
👉 መቀሌ - አብርሃ ካስትል፣ ቀበሌ 18፣ ዲያስፖራ፣ ማጂክ ስኩል፣ ደብረዳሞ፣ ሰማዕታት ሀውልት፣ ዲደብሊው ቢሮ፣ ፕላኔት ሆቴል፣ ጅብሩክ፣ እንደማርያም ጉግሳ አካባቢ፣ መቀሌ ሆስፒታል፣ ቀበሌ 14፣15፣16ና 17፣ አይናለም አካባቢ
✅ ከጠዋቱ 12፡00 – 6፡43
👉ሽሬ - ክሳደገባ፣ እንዳባጉና፣ ዛና፣ ምይሃንሴ፣ ደደቢት፣ ማይሊ፣ ሽራሮ፣ አዲሀገረይ፣ አዲነብሬድ፣ አዲዳእሮ፣ ማይፀብሪ፣ አዲአርካይ፣ አዲገብሩ እና አካባያቸው ላይ ኃይል ይቋረጣል።
ስለሆነም በተጠቀሱት አካባቢዎች የምትገኙ የተከበራችሁ ደንበኞቻችን የጥገና ሥራው ተጠናቆ የኃይል አቅርቦቱ እስኪመለስ ድረስ በትዕግስት እንድትጠብቁን እንጠይቃለን፡፡
#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት
4 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) በናይጄሪያ የቀድሞ የአቪዬሽን ሚኒስትር ሀዲ ሲሪካ የሙስና ክስ የፍርድ ሂደት ላይ "ናይጄሪያ ኤር" የተሰኘውን አዲስ ብሔራዊ አየር መንገድ ለማስተዋወቅ የኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላን ለጥቂት ቀናት ጥቅም ላይ ውሎ እንደነበር አንድ ምስክር ለአቡጃ ፍርድ ቤት አስረዱ።
የናይጄሪያ የኢኮኖሚ እና የፋይናንስ ወንጀሎች ኮሚሽን መርማሪ እና የዓቃቤ ሕግ 12ኛ ምስክር የሆኑት ክሪስቶፈር ኦዶፊን ለፍርድ ቤቱ እንዳብራሩት.. አውሮፕላኑ ከሜይ 27 እስከ 29 ቀን 2023 ድረስ ብቻ በናይጄሪያ ቆይታ አድርጓል። በዚህ አጭር ጊዜ ውስጥ በላዩ ላይ "ናይጄሪያ ኤር" የሚል የብራንድ ጽሑፍ ተለጥፎበት ለሕዝብ ዕይታ ከቀረበ በኋላ፣ ወዲያውኑ ወደ ኢትዮጵያ ተመልሶ ጽሑፉ እንዲነሳ ተደርጓል። ምስክሩ አክለውም ይህ አሠራር ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ጋር በተደረገ የቻርተር (የኪራይ) ስምምነት የተፈጸመ መሆኑን እና የበረራ አባላቱም የኢትዮጵያ አየር መንገድን የደንብ ልብስ ለብሰው እንደነበር ገልጸዋል።
አቃቤ ሕግ ይህ ድርጊት የቀድሞው ሚኒስትር በስልጣን ዘመናቸው ከብሔራዊ አየር መንገዱ ምሥረታ ጋር በተያያዘ ከፈጸሙት ሰፊ የኮንትራት አሰጣጥ ማጭበርበር አንዱ አካል መሆኑን ክስ አቅርቧል። ይሁን እንጂ የቀድሞው ሚኒስትር ሀዲ ሲሪካ፣ አብረዋቸው የተከሰሱት ልጃቸው ፋጢማ ሲሪካ፣ አማቻቸው እና ሌሎች ተከሳሾች የቀረበባቸውን የሙስና ክስ ሙሉ በሙሉ አስተባብለዋል። በዲጂታል እና በሰነድ የተደገፉ ማስረጃዎችን የተቀበለው ፍርድ ቤቱም፣ ቀጣዩን የፍርድ ሂደት ለጁን 10 አስተላልፏል።
የናይጄሪያ የኢኮኖሚ እና የፋይናንስ ወንጀሎች ኮሚሽን መርማሪ እና የዓቃቤ ሕግ 12ኛ ምስክር የሆኑት ክሪስቶፈር ኦዶፊን ለፍርድ ቤቱ እንዳብራሩት.. አውሮፕላኑ ከሜይ 27 እስከ 29 ቀን 2023 ድረስ ብቻ በናይጄሪያ ቆይታ አድርጓል። በዚህ አጭር ጊዜ ውስጥ በላዩ ላይ "ናይጄሪያ ኤር" የሚል የብራንድ ጽሑፍ ተለጥፎበት ለሕዝብ ዕይታ ከቀረበ በኋላ፣ ወዲያውኑ ወደ ኢትዮጵያ ተመልሶ ጽሑፉ እንዲነሳ ተደርጓል። ምስክሩ አክለውም ይህ አሠራር ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ጋር በተደረገ የቻርተር (የኪራይ) ስምምነት የተፈጸመ መሆኑን እና የበረራ አባላቱም የኢትዮጵያ አየር መንገድን የደንብ ልብስ ለብሰው እንደነበር ገልጸዋል።
አቃቤ ሕግ ይህ ድርጊት የቀድሞው ሚኒስትር በስልጣን ዘመናቸው ከብሔራዊ አየር መንገዱ ምሥረታ ጋር በተያያዘ ከፈጸሙት ሰፊ የኮንትራት አሰጣጥ ማጭበርበር አንዱ አካል መሆኑን ክስ አቅርቧል። ይሁን እንጂ የቀድሞው ሚኒስትር ሀዲ ሲሪካ፣ አብረዋቸው የተከሰሱት ልጃቸው ፋጢማ ሲሪካ፣ አማቻቸው እና ሌሎች ተከሳሾች የቀረበባቸውን የሙስና ክስ ሙሉ በሙሉ አስተባብለዋል። በዲጂታል እና በሰነድ የተደገፉ ማስረጃዎችን የተቀበለው ፍርድ ቤቱም፣ ቀጣዩን የፍርድ ሂደት ለጁን 10 አስተላልፏል።
4 days ago
የቀድሞው የናይጄሪያ አቪዬሽን ሚኒስትር የኢትዮጵያ አየር መንገድን አውሮፕላን ለ3 ቀናት ብቻ ተከራይተው የውሸት ምረቃ ማድረጋቸው ተጋለጠ
የናይጄሪያ የኢኮኖሚ እና የፋይናንስ ወንጀሎች ኮሚሽን (EFCC) ባደረገው ከፍተኛ ምርመራ፣ የቀድሞው የአቪዬሽን ሚኒስትር ሀዲ አቡበከር ሲሪካ "ናይጄሪያ ኤር" የተባለውን አዲስ ብሔራዊ አየር መንገድ ስራ እንደጀመረ ለማስመሰል የፈጸሙት መጠነ-ሰፊ ማጭበርበር ፍርድ ቤት ላይ ይፋ ሆነ።
ሚኒስትሩ አየር መንገዱ መቋቋሙን ለሕዝብ ለማሳየት ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ጋር የ3 ቀናት ብቻ የኪራይ ስምምነት ማድረጋቸውን የኮሚሽኑ መርማሪዎች ለፍርድ ቤት አስረድተዋል።
በአጠቃላይ 20 ቢሊዮን ናይራ የሚገመት የዕምነት ማጉደል እና የሙስና ወንጀል ፈጽመዋል የተባሉት ሚኒስትሩ፣ አውሮፕላኑ የቀድሞው ፕሬዝዳንት ሙሀማዱ ቡሀሪ ስልጣን በለቀቁበት ዕለት (ግንቦት 29 ቀን 2023) ሀገሪቱን ለቆ እንዲወጣ አስቀድመው ውል አዘጋጅተው ነበር።
አውሮፕላኑ አቡጃ አውሮፕላን ማረፊያ በደረሰበት ወቅትም፣ የናይጄሪያ ኤርን የደንብ ልብስ የለበሱ የሀገር ውስጥ ሞዴሎች በገንዘብ ተከፍሏቸው የውሸት የማስተዋወቂያ ፎቶዎች እንዲነሱ መደረጉን መርማሪው በምስክርነታቸው ጠቅሰዋል።
ይህን ተከትሎ የቀድሞው ሚኒስትር ሀዲ ሲሪካ፣ ልጃቸው፣ አማቻቸው እና "አል ቡራቅ ግሎባል ኢንቨስትመንት" የተባለ ኩባንያ በቁጥጥር ስር ውለዋል። ተከሳሾቹ የስልጣን አለአግባብ መገልገያ እና ከ2 ቢሊዮን ናይራ በላይ የህዝብ ሀብት ማባከንን ጨምሮ ስድስት የወንጀል ክሶች ቀርበውባቸዋል።
በተጨማሪም ምርመራው እንደሚያሳየው፣ መጀመሪያ ላይ የናይጄሪያ ኤርን ለማቋቋም "ቲያናኤሮ ናይጄሪያ ሊሚትድ" ለተባለ ኩባንያ ተሰጥቶ የነበረው የ299 ሚሊዮን ናይሪያ ውል፣ በሚኒስትሩ ቀጥተኛ ትዕዛዝ ወደ 599 ሚሊዮን ናይራ ከፍ እንዲል ተደርጓል።
ይህ የሙስና ሰንሰለት ሊደረስበት የቻለው የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ቋሚ ጸሐፊ የነበሩትን ግለሰብ ስልክ በመፈተሽ ሲሆን፣ ሚኒስትሩ በወቅቱ በስፔን ሆነው ውሉ ለተጠቀሰው ኩባንያ እንዲሰጥ ያስተላለፉት የድምፅ መልዕክት በማስረጃነት ተገኝቷል።
ክሱ በአሁኑ ወቅት በናይጄሪያ ከፍተኛ ፍርድ ቤት እየታየ ይገኛል።
የናይጄሪያ የኢኮኖሚ እና የፋይናንስ ወንጀሎች ኮሚሽን (EFCC) ባደረገው ከፍተኛ ምርመራ፣ የቀድሞው የአቪዬሽን ሚኒስትር ሀዲ አቡበከር ሲሪካ "ናይጄሪያ ኤር" የተባለውን አዲስ ብሔራዊ አየር መንገድ ስራ እንደጀመረ ለማስመሰል የፈጸሙት መጠነ-ሰፊ ማጭበርበር ፍርድ ቤት ላይ ይፋ ሆነ።
ሚኒስትሩ አየር መንገዱ መቋቋሙን ለሕዝብ ለማሳየት ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ጋር የ3 ቀናት ብቻ የኪራይ ስምምነት ማድረጋቸውን የኮሚሽኑ መርማሪዎች ለፍርድ ቤት አስረድተዋል።
በአጠቃላይ 20 ቢሊዮን ናይራ የሚገመት የዕምነት ማጉደል እና የሙስና ወንጀል ፈጽመዋል የተባሉት ሚኒስትሩ፣ አውሮፕላኑ የቀድሞው ፕሬዝዳንት ሙሀማዱ ቡሀሪ ስልጣን በለቀቁበት ዕለት (ግንቦት 29 ቀን 2023) ሀገሪቱን ለቆ እንዲወጣ አስቀድመው ውል አዘጋጅተው ነበር።
አውሮፕላኑ አቡጃ አውሮፕላን ማረፊያ በደረሰበት ወቅትም፣ የናይጄሪያ ኤርን የደንብ ልብስ የለበሱ የሀገር ውስጥ ሞዴሎች በገንዘብ ተከፍሏቸው የውሸት የማስተዋወቂያ ፎቶዎች እንዲነሱ መደረጉን መርማሪው በምስክርነታቸው ጠቅሰዋል።
ይህን ተከትሎ የቀድሞው ሚኒስትር ሀዲ ሲሪካ፣ ልጃቸው፣ አማቻቸው እና "አል ቡራቅ ግሎባል ኢንቨስትመንት" የተባለ ኩባንያ በቁጥጥር ስር ውለዋል። ተከሳሾቹ የስልጣን አለአግባብ መገልገያ እና ከ2 ቢሊዮን ናይራ በላይ የህዝብ ሀብት ማባከንን ጨምሮ ስድስት የወንጀል ክሶች ቀርበውባቸዋል።
በተጨማሪም ምርመራው እንደሚያሳየው፣ መጀመሪያ ላይ የናይጄሪያ ኤርን ለማቋቋም "ቲያናኤሮ ናይጄሪያ ሊሚትድ" ለተባለ ኩባንያ ተሰጥቶ የነበረው የ299 ሚሊዮን ናይሪያ ውል፣ በሚኒስትሩ ቀጥተኛ ትዕዛዝ ወደ 599 ሚሊዮን ናይራ ከፍ እንዲል ተደርጓል።
ይህ የሙስና ሰንሰለት ሊደረስበት የቻለው የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ቋሚ ጸሐፊ የነበሩትን ግለሰብ ስልክ በመፈተሽ ሲሆን፣ ሚኒስትሩ በወቅቱ በስፔን ሆነው ውሉ ለተጠቀሰው ኩባንያ እንዲሰጥ ያስተላለፉት የድምፅ መልዕክት በማስረጃነት ተገኝቷል።
ክሱ በአሁኑ ወቅት በናይጄሪያ ከፍተኛ ፍርድ ቤት እየታየ ይገኛል።
4 days ago
የዲጂታል ኢኮኖሚ አዲስ ምዕራፍ - ከስትራቴጂ ወደ ስኬት
***********************
(የዕለቱ መልዕክት)
ዛሬ ዓለማችን በቴክኖሎጂ እና በኢኖቬሽን ፈጣን ግስጋሴ ውስጥ ትገኛለች። ኢትዮጵያም ይህንን ዓለም አቀፋዊ እውነት በውል በመገንዘብ፣ ሁለንተናዊ ኢኮኖሚዋን ከመሠረቱ የሚቀይር ታሪካዊ የዲጂታል ሽግግር እያከናወነች ትገኛለች።
በተለይም ባለፉት አምስት ዓመታት ሀገራችን ያለባትን ዘላቂ የቢሮክራሲ እና የኢኮኖሚ ፈተናዎች ለመቅረፍ ዲጂታላይዜሽንን እንደ ዋነኛ ስትራቴጂያዊ መሣሪያ በመውሰድ እየሠራችበት ትገኛለች።
ይህ ጉዞ የሀገርን የልማት ምሰሶ በጽኑ መሠረት ላይ የሚያጸና የመንግሥት የረጅም ጊዜ ቁርጠኝነት ማሳያ ነው ብለን እናምናለን።
በአንድ ወቅት የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ እንደ ሩቅ ሕልም ይታይ እንደነበር አይዘነጋም፤ ባለፉት አምስት ዓመታት በተከናወኑት መሠረታዊ ሥራዎች ግን ዛሬ ላይ ሊሻር በማይችል እውነታ ላይ የቆመ መሠረት ተጥሏል።
መንግሥት ያደረጋቸው ሰፊ የፖሊሲ እና የሕግ ማሻሻያዎች “ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025” ስትራቴጂን በስኬት ለማጠናቀቅ አስችለዋል።
አሁን ደግሞ የሀገራችንን የትራንስፎርሜሽን ጉዞ ይበልጥ የሚያፋጥን እና ይበልጥ ስኬታማ የሚያደርገው “ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030” የተሰኘው ብሔራዊ ስትራቴጂ ፀድቆ ወደ ሥራ እንዲገባ መደረጉ የሂደቱን ቀጣይነት ያረጋግጣል።
ከዚህ ጎን ለጎን የሰው ሠራሽ አስተውሎት ኢንስቲትዩት መቋቋም ለችግር ፈቺ የቴክኖሎጂ መፍትሔዎች መበልጸግ ምቹ ሁኔታን መፍጠሩ የሚበረታታ እርምጃ ነው።
በዚህ ዘመናዊ የታሪክ እጥፋት ውስጥ የ“ፋይዳ” ብሔራዊ የዲጂታል መታወቂያ ፕሮግራም እና የ“ኢትዮኮደርስ” ኢኒሼቲቭ ሚና እጅግ የላቀ ነው።
የዲጂታል መታወቂያ ለኢኮኖሚው ግንባታ ልክ እንደ ቤት መሠረት ነው። እስከ 90 ሚሊዮን ዜጎችን በሥርዓቱ ውስጥ ለማቀፍ የታቀደው ይህ ግዙፍ መርሐ ግብር ለባንክ፣ ለፋይናንስ፣ ለንግድ እንቅስቃሴ እና ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ ወሳኝ ምሰሶ ነው።
“የቆጠሩት እህል አያልቅም” እንደሚባለው የሀገርን የሰው ኃይል በዕውቀት ሳያደራጁ ዘላቂ ስኬትን ማሰብ አይቻልም። በመሆኑም በ“ኢትዮኮደርስ” ኢኒሼቲቭ 5 ሚሊዮን ዜጎች የዲጂታል ክህሎት ሥልጠና እንዲያገኙ ማድረግ የነገዋን የበለጸገች ኢትዮጵያ የሚረከቡ ባለሙያዎችን ለማፍራት የተጣለ ታላቅ መሠረት ነው።
የአገልግሎት አሰጣጥን ለማዘመን በሁሉም አካባቢዎች እየተገነባ ያለው “የመሶብ” የአንድ ማዕከል አገልግሎትም የተንዛዛ ቢሮክራሲን እና የዜጎችን እንግልት በማስቀረት የመንግሥትን ግልጽነት እና ተጠያቂነት በከፍተኛ ደረጃ አሳድጎታል። ይህ ዓይነቱ አሠራር ሙስና እና ብክነትን በዘላቂነት ለመከላከል የሚያስችል አስተማማኝ ተቋማዊ አቅም ይፈጥራል።
በፋይናንስ ዘርፍም ቢሆን በ2017 በጀት ዓመት ብቻ በዲጂታል የተከናወነው የግብይት ዋጋ 16 ትሪሊዮን ብር መድረሱ የዲጂታል ኢኮኖሚው ምን ያህል ውጤታማ እና ተደራሽ እየሆነ ለመምጣቱ ሕያው ማሳያ ነው።
ይህ ስኬት ዝቅተኛ ገቢ ያላቸው ዜጎች እና ጥቃቅን ኢንተርፕራይዞች በቀላሉ የብድር እና የቁጠባ አገልግሎት እንዲያገኙ በማድረግ የፋይናንስ አካታችነትን በተግባር አረጋግጧል።
ለወደፊቱም መሠረታዊ የመንግሥት አገልግሎቶችን ሙሉ በሙሉ በዲጂታል ፕላትፎርሞች ተደራሽ ለማድረግ የታቀደው ዕቅድ የሀገራችንን የነገ ገጽታ በእጅጉ የሚቀይር ነው።
መንግሥት የሳይበር ሉዓላዊነትን በማረጋገጥ እና የስታርትአፕ ሥነ ምኅዳርን በማጠናከር፣ የዲጂታል ሽግግር ሂደቱን አስተማማኝ እና ደኅንነቱ የተጠበቀ እያደረገው ይገኛል።
በአጠቃላይ ይህ ታሪካዊ ጉዞ የዜጎችን የዕለት ተዕለት ኑሮ የሚያቀልል፣ ሀገራችንን በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ የሚያደርግ እና የኢኮኖሚ ልማታችንን ከሕልም ወደ እውነት የለወጠ የጋራ ብሔራዊ ስኬታችን በመሆኑ ሁሉም አካላት ለስኬቱ የበኩላቸውን ድርሻ ሊወጡ ይገባል።
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
#ethiopia #ebc #digitalethiopia #5millioncoders #success #𝐃𝐢𝐠𝐢𝐭𝐚𝐥𝐄𝐜𝐨𝐧𝐨𝐦𝐲
***********************
(የዕለቱ መልዕክት)
ዛሬ ዓለማችን በቴክኖሎጂ እና በኢኖቬሽን ፈጣን ግስጋሴ ውስጥ ትገኛለች። ኢትዮጵያም ይህንን ዓለም አቀፋዊ እውነት በውል በመገንዘብ፣ ሁለንተናዊ ኢኮኖሚዋን ከመሠረቱ የሚቀይር ታሪካዊ የዲጂታል ሽግግር እያከናወነች ትገኛለች።
በተለይም ባለፉት አምስት ዓመታት ሀገራችን ያለባትን ዘላቂ የቢሮክራሲ እና የኢኮኖሚ ፈተናዎች ለመቅረፍ ዲጂታላይዜሽንን እንደ ዋነኛ ስትራቴጂያዊ መሣሪያ በመውሰድ እየሠራችበት ትገኛለች።
ይህ ጉዞ የሀገርን የልማት ምሰሶ በጽኑ መሠረት ላይ የሚያጸና የመንግሥት የረጅም ጊዜ ቁርጠኝነት ማሳያ ነው ብለን እናምናለን።
በአንድ ወቅት የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ እንደ ሩቅ ሕልም ይታይ እንደነበር አይዘነጋም፤ ባለፉት አምስት ዓመታት በተከናወኑት መሠረታዊ ሥራዎች ግን ዛሬ ላይ ሊሻር በማይችል እውነታ ላይ የቆመ መሠረት ተጥሏል።
መንግሥት ያደረጋቸው ሰፊ የፖሊሲ እና የሕግ ማሻሻያዎች “ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025” ስትራቴጂን በስኬት ለማጠናቀቅ አስችለዋል።
አሁን ደግሞ የሀገራችንን የትራንስፎርሜሽን ጉዞ ይበልጥ የሚያፋጥን እና ይበልጥ ስኬታማ የሚያደርገው “ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030” የተሰኘው ብሔራዊ ስትራቴጂ ፀድቆ ወደ ሥራ እንዲገባ መደረጉ የሂደቱን ቀጣይነት ያረጋግጣል።
ከዚህ ጎን ለጎን የሰው ሠራሽ አስተውሎት ኢንስቲትዩት መቋቋም ለችግር ፈቺ የቴክኖሎጂ መፍትሔዎች መበልጸግ ምቹ ሁኔታን መፍጠሩ የሚበረታታ እርምጃ ነው።
በዚህ ዘመናዊ የታሪክ እጥፋት ውስጥ የ“ፋይዳ” ብሔራዊ የዲጂታል መታወቂያ ፕሮግራም እና የ“ኢትዮኮደርስ” ኢኒሼቲቭ ሚና እጅግ የላቀ ነው።
የዲጂታል መታወቂያ ለኢኮኖሚው ግንባታ ልክ እንደ ቤት መሠረት ነው። እስከ 90 ሚሊዮን ዜጎችን በሥርዓቱ ውስጥ ለማቀፍ የታቀደው ይህ ግዙፍ መርሐ ግብር ለባንክ፣ ለፋይናንስ፣ ለንግድ እንቅስቃሴ እና ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ ወሳኝ ምሰሶ ነው።
“የቆጠሩት እህል አያልቅም” እንደሚባለው የሀገርን የሰው ኃይል በዕውቀት ሳያደራጁ ዘላቂ ስኬትን ማሰብ አይቻልም። በመሆኑም በ“ኢትዮኮደርስ” ኢኒሼቲቭ 5 ሚሊዮን ዜጎች የዲጂታል ክህሎት ሥልጠና እንዲያገኙ ማድረግ የነገዋን የበለጸገች ኢትዮጵያ የሚረከቡ ባለሙያዎችን ለማፍራት የተጣለ ታላቅ መሠረት ነው።
የአገልግሎት አሰጣጥን ለማዘመን በሁሉም አካባቢዎች እየተገነባ ያለው “የመሶብ” የአንድ ማዕከል አገልግሎትም የተንዛዛ ቢሮክራሲን እና የዜጎችን እንግልት በማስቀረት የመንግሥትን ግልጽነት እና ተጠያቂነት በከፍተኛ ደረጃ አሳድጎታል። ይህ ዓይነቱ አሠራር ሙስና እና ብክነትን በዘላቂነት ለመከላከል የሚያስችል አስተማማኝ ተቋማዊ አቅም ይፈጥራል።
በፋይናንስ ዘርፍም ቢሆን በ2017 በጀት ዓመት ብቻ በዲጂታል የተከናወነው የግብይት ዋጋ 16 ትሪሊዮን ብር መድረሱ የዲጂታል ኢኮኖሚው ምን ያህል ውጤታማ እና ተደራሽ እየሆነ ለመምጣቱ ሕያው ማሳያ ነው።
ይህ ስኬት ዝቅተኛ ገቢ ያላቸው ዜጎች እና ጥቃቅን ኢንተርፕራይዞች በቀላሉ የብድር እና የቁጠባ አገልግሎት እንዲያገኙ በማድረግ የፋይናንስ አካታችነትን በተግባር አረጋግጧል።
ለወደፊቱም መሠረታዊ የመንግሥት አገልግሎቶችን ሙሉ በሙሉ በዲጂታል ፕላትፎርሞች ተደራሽ ለማድረግ የታቀደው ዕቅድ የሀገራችንን የነገ ገጽታ በእጅጉ የሚቀይር ነው።
መንግሥት የሳይበር ሉዓላዊነትን በማረጋገጥ እና የስታርትአፕ ሥነ ምኅዳርን በማጠናከር፣ የዲጂታል ሽግግር ሂደቱን አስተማማኝ እና ደኅንነቱ የተጠበቀ እያደረገው ይገኛል።
በአጠቃላይ ይህ ታሪካዊ ጉዞ የዜጎችን የዕለት ተዕለት ኑሮ የሚያቀልል፣ ሀገራችንን በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ የሚያደርግ እና የኢኮኖሚ ልማታችንን ከሕልም ወደ እውነት የለወጠ የጋራ ብሔራዊ ስኬታችን በመሆኑ ሁሉም አካላት ለስኬቱ የበኩላቸውን ድርሻ ሊወጡ ይገባል።
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
#ethiopia #ebc #digitalethiopia #5millioncoders #success #𝐃𝐢𝐠𝐢𝐭𝐚𝐥𝐄𝐜𝐨𝐧𝐨𝐦𝐲
5 days ago
በነዳጅ ሙስና ወንጀል ተጠርጥረው በነበሩ አምስት ተከሳሾች ላይ የቀረበው ክስ እንዲቋረጥ ተወሰነ
#ethiopia | በነዳጅ እጥረት መከሰት እና በከባድ የሙስና ወንጀል ተሳትፈዋል በሚል ክስ ተመስርቶባቸው በነበሩ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች እና ነጋዴዎች ላይ የቀረበው ሦስተኛው የክስ መዝገብ እንዲቋረጥ የፍትሕ ሚኒስቴር ትዕዛዝ አስተላልፏል።
ይህ የክስ መቋረጥ ውሳኔ የተላለፈው የነዳጅና ኢነርጂ ባለሥልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር የሆኑትን አቶ ዲባራ ፉፋን እና በፌደራል ፖሊስ አማካኝነት የይፈለጋሉ ማስታወቂያ የወጣባቸውን ሁለት ተከሳሾችን ጨምሮ በአጠቃላይ በአምስት ተከሳሾች ላይ ነው።
የፍትሕ ሚኒስቴር የሙስና ወንጀል ጉዳዮች ዐቃቤ ሕግ ዳይሬክቶሬት ግንቦት 28 ቀን 2018 ዓ.ም በጻፈው ይፋዊ ደብዳቤ እንዳስታወቀው፣ ውሳኔው የተላለፈው ከ9ኛ እና ከ10ኛ ተከሳሾች የቀረበን አቤቱታ መሠረት በማድረግ ነው።
የቀረበው አቤቱታ ከተመረመረ በኋላ ምክንያቱ አሳማኝ ሆኖ በመገኘቱ እና በተከሳሾቹ ላይ የተሰነዘረውን የጥፋተኝነት ክስ ለማስረዳት የሚያስችል በቂ ማስረጃ ባለመኖሩ ክሱ እንዲቋረጥ ተወስኗል።
ይህ እርምጃ የተወሰደው በአዋጅ ቁጥር 943/2008 አንቀጽ 6 ንዑስ አንቀጽ 3(ሀ) እና በፍትሕ ሚኒስቴር የወንጀል መዝገቦች ውሳኔ አሰጣጥ መመሪያ መሠረት ነው።
በዚህም መሠረት ክሳቸው እንዲቋረጥ የተደረገላቸው ተከሳሾች የሚከተሉት ናቸው
የነዳጅና ኢነርጂ ባለሥልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ዲባራ ፉፋ (1ኛ ተከሳሽ)
አቶ ይላቅ አወቀ (4ኛ ተከሳሽ)
አቶ አበላ ግዛው (5ኛ ተከሳሽ)
አቶ ይልቃል የኔሰው (9ኛ ተከሳሽ)
የኛ ፔትሮሊየም ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር (10ኛ ተከሳሽ)
ቀደም ሲል ለተቋማት ያለአግባብ የነዳጅ ግዥ ፈቃድ በመስጠት እና የነዳጅ እጥረት እንዲከሰት በማድረግ በመንግሥት ላይ የከባድ ሙስና ወንጀል ፈጽመዋል በሚል በ13 ግለሰቦችና ድርጅቶች ላይ ክስ ቀርቦ የነበረ ሲሆን፣ ከእነዚህም መካከል ሦስተኛው የክስ ዝርዝር የኛ ፔትሮሊየም ድርጅት ከሕግ አግባብ ውጭ የነዳጅ አከፋፋይነት ፈቃድ እንዲያገኝ በማድረግ በመንግሥት ላይ ከ21.3 ሚሊዮን ብር በላይ ጉዳት ደርሷል የሚል ነበር።
የጠቅላይ አቃቤ ሕግ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ቸርነት ሆርዶፋ የፈረሙበት እና ለፍትሕ ሚኒስቴር ሚኒስትር ወይዘሮ ሃና አርአያሥላሴ በግልባጭ እንዲያውቁት የተደረገው ይህ የክስ መቋረጥ ትዕዛዝ ለፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የልደታ ምድብ 3ኛ የሙስና ጉዳዮች ወንጀል ችሎት ቀርቧል። ፍርድ ቤቱ የቀረበውን ትዕዛዝ መርምሮ ውሳኔ ይሰጣል ተብሎ ይጠበቃል።
የአቶ ይልቃል የኔሰው እና የየኛ ፔትሮሊየም ጠበቃ የሆኑት አቶ ወንድማገኝ ጸጋዬ እንደገለጹት፣ ውሳኔው ለችሎት የቀረበው ቀደም ብሎ ከተሰጠው የሰኔ 18 ቀን 2018 ዓ.ም የችሎት ቀጠሮ በፊት በመሆኑ በውስጥ ውሳኔ ይሰጥበታል ተብሎ ይታመናል።
ችሎቱ ትዕዛዙን ተቀብሎ ውሳኔ ሲያስተላልፍ በሕግ ጥላ ሥር የሚገኙት አቶ ይላቅ አወቀ፣ አቶ አበላ ግዛው እና አቶ ይልቃል የኔሰው የፍርድ ሂደታቸው ተቋርጦ ነጻ እንደሚሆኑ ጠበቃው አረጋግጠዋል።
ይሁን እንጂ በመዝገቡ አንደኛ ተከሳሽ የሆኑት የነዳጅና ኢነርጂ ባለሥልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ዲባራ ፉፋ፣ ሦስተኛው ክሳቸው እንዲቋረጥላቸው ቢወሰንም በመዝገቡ ላይ የተካተቱ ሌሎች ተጨማሪ ክሶች ስላሉባቸው የፍርድ ቤት ሂደታቸው የሚቀጥል ይሆናል።
#fuelcrisis #corruptioncase #ethiopiancourt #justice #ministryofjustice #legalnews #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | በነዳጅ እጥረት መከሰት እና በከባድ የሙስና ወንጀል ተሳትፈዋል በሚል ክስ ተመስርቶባቸው በነበሩ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች እና ነጋዴዎች ላይ የቀረበው ሦስተኛው የክስ መዝገብ እንዲቋረጥ የፍትሕ ሚኒስቴር ትዕዛዝ አስተላልፏል።
ይህ የክስ መቋረጥ ውሳኔ የተላለፈው የነዳጅና ኢነርጂ ባለሥልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር የሆኑትን አቶ ዲባራ ፉፋን እና በፌደራል ፖሊስ አማካኝነት የይፈለጋሉ ማስታወቂያ የወጣባቸውን ሁለት ተከሳሾችን ጨምሮ በአጠቃላይ በአምስት ተከሳሾች ላይ ነው።
የፍትሕ ሚኒስቴር የሙስና ወንጀል ጉዳዮች ዐቃቤ ሕግ ዳይሬክቶሬት ግንቦት 28 ቀን 2018 ዓ.ም በጻፈው ይፋዊ ደብዳቤ እንዳስታወቀው፣ ውሳኔው የተላለፈው ከ9ኛ እና ከ10ኛ ተከሳሾች የቀረበን አቤቱታ መሠረት በማድረግ ነው።
የቀረበው አቤቱታ ከተመረመረ በኋላ ምክንያቱ አሳማኝ ሆኖ በመገኘቱ እና በተከሳሾቹ ላይ የተሰነዘረውን የጥፋተኝነት ክስ ለማስረዳት የሚያስችል በቂ ማስረጃ ባለመኖሩ ክሱ እንዲቋረጥ ተወስኗል።
ይህ እርምጃ የተወሰደው በአዋጅ ቁጥር 943/2008 አንቀጽ 6 ንዑስ አንቀጽ 3(ሀ) እና በፍትሕ ሚኒስቴር የወንጀል መዝገቦች ውሳኔ አሰጣጥ መመሪያ መሠረት ነው።
በዚህም መሠረት ክሳቸው እንዲቋረጥ የተደረገላቸው ተከሳሾች የሚከተሉት ናቸው
የነዳጅና ኢነርጂ ባለሥልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ዲባራ ፉፋ (1ኛ ተከሳሽ)
አቶ ይላቅ አወቀ (4ኛ ተከሳሽ)
አቶ አበላ ግዛው (5ኛ ተከሳሽ)
አቶ ይልቃል የኔሰው (9ኛ ተከሳሽ)
የኛ ፔትሮሊየም ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር (10ኛ ተከሳሽ)
ቀደም ሲል ለተቋማት ያለአግባብ የነዳጅ ግዥ ፈቃድ በመስጠት እና የነዳጅ እጥረት እንዲከሰት በማድረግ በመንግሥት ላይ የከባድ ሙስና ወንጀል ፈጽመዋል በሚል በ13 ግለሰቦችና ድርጅቶች ላይ ክስ ቀርቦ የነበረ ሲሆን፣ ከእነዚህም መካከል ሦስተኛው የክስ ዝርዝር የኛ ፔትሮሊየም ድርጅት ከሕግ አግባብ ውጭ የነዳጅ አከፋፋይነት ፈቃድ እንዲያገኝ በማድረግ በመንግሥት ላይ ከ21.3 ሚሊዮን ብር በላይ ጉዳት ደርሷል የሚል ነበር።
የጠቅላይ አቃቤ ሕግ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ቸርነት ሆርዶፋ የፈረሙበት እና ለፍትሕ ሚኒስቴር ሚኒስትር ወይዘሮ ሃና አርአያሥላሴ በግልባጭ እንዲያውቁት የተደረገው ይህ የክስ መቋረጥ ትዕዛዝ ለፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የልደታ ምድብ 3ኛ የሙስና ጉዳዮች ወንጀል ችሎት ቀርቧል። ፍርድ ቤቱ የቀረበውን ትዕዛዝ መርምሮ ውሳኔ ይሰጣል ተብሎ ይጠበቃል።
የአቶ ይልቃል የኔሰው እና የየኛ ፔትሮሊየም ጠበቃ የሆኑት አቶ ወንድማገኝ ጸጋዬ እንደገለጹት፣ ውሳኔው ለችሎት የቀረበው ቀደም ብሎ ከተሰጠው የሰኔ 18 ቀን 2018 ዓ.ም የችሎት ቀጠሮ በፊት በመሆኑ በውስጥ ውሳኔ ይሰጥበታል ተብሎ ይታመናል።
ችሎቱ ትዕዛዙን ተቀብሎ ውሳኔ ሲያስተላልፍ በሕግ ጥላ ሥር የሚገኙት አቶ ይላቅ አወቀ፣ አቶ አበላ ግዛው እና አቶ ይልቃል የኔሰው የፍርድ ሂደታቸው ተቋርጦ ነጻ እንደሚሆኑ ጠበቃው አረጋግጠዋል።
ይሁን እንጂ በመዝገቡ አንደኛ ተከሳሽ የሆኑት የነዳጅና ኢነርጂ ባለሥልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ዲባራ ፉፋ፣ ሦስተኛው ክሳቸው እንዲቋረጥላቸው ቢወሰንም በመዝገቡ ላይ የተካተቱ ሌሎች ተጨማሪ ክሶች ስላሉባቸው የፍርድ ቤት ሂደታቸው የሚቀጥል ይሆናል።
#fuelcrisis #corruptioncase #ethiopiancourt #justice #ministryofjustice #legalnews #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
Sponsored by
Surafel
5 days ago
የኢትዮጵያ ነዳጅና ኢነርጅ ባለስልጣን የቀድሞ ም/ዋና ዳይሬክተርን ዲቦራ ፉፋን ጨምሮ የ5 ተከሳሾች ላይ ቀርቦ የነበረው ከባድ የሙስና ክስ ተቋረጠ።
የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የልደታ ምድብ 3ኛ የሙስና ጉዳዮች ወንጀል ችሎት "በገበያ ላይ የነዳጅ እጥረት እንዲከሰት አድርገዋል"የተባሉ የኢትዮጵያ ነዳጅና ኢነርጂ ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተርን ጨምሮ በ13 ተከሳሾች ላይ የተመሰረተውን የከባድ ሙስና ወንጀል ክስ የ5ቱ እንዲቋረጥ መደረጉን አስታውቋል፡፡
የክስ መቃወሚያ እንዲያቀርቡ ሰኔ 1 ቀን 2018 ዓ.ም ቀጠሮ ተይዞ የነበረ ሲሆን በችሎቱ የክስ መቃወሚያውና የአቃቢ ህግ መልስ ተነቦ የክስ ማሻሻያያ እንዲደረግና ባልቀረቡ ተከሳሾች በጋዜጣ እንዲጠሩ ፍ/ቤቱ አዝዞ ለሰኔ 18/ 2018 ዓ/ም ቀጠሮ ተሰጥቶ ነበር።
ይሁንና የ5ቱ ተከሳሾች ማለትም 1ኛ ተከሳሽ ዲቦራ ፉፋ ፣4ኛ ተከሳሽ ይላቅ አወቀ፣ 5ኛ ተከሳሽ አበላ ግዛው እንዲሁም ፖሊስ አፋልጉኝ አውጥቶባቸው የነበረው 9ኛ ተከሳሽ ይልቃል የኔሰው እና 10 ተከሳሽ የኛ ፔትሮሊየም ኀ/የ/ግ/ ማህበር ክሳቸው እንዲቋረጥ ተወስኗል፡፡
ክሱ የተቋረጠው፣ ፍትህ ሚኒስቴር ክሱ አንዲቋረጥ አቤቱታ በማቅቡ አንደሆነ ፍረድ ቤቱ ጠቅሷል፡፡
4ኛ ተከሣሽ አቶ ይላቅ እወቀ ይብለው እና 5ኛ ተከሣሽ አቶ አበላ ግዛው በሪ በዚህ የክስ መዝገብ የቀረበባቸው 3ኛ ክስን በተመለከተ ብቻ በመሆኑና ክሱ የተቋረጠ ስለሆነ የአዲስ አበባ የቂሊንጦ ማረሚያ ቤት ተከሳሾች በሌላ ወንጀል የማይፈለጉ መሆኑን በማረጋገጥ ከእስር እንዲለቃቸው የእስር መፍቻ ትዕዛዝ እንዲፃፍ ታዟል።
9ኛ ተከሣሽ ይልቃል የኔሰው ዘለቀ እና 10ኛ ተከሣሽ የኛ ፔትሮሊየም ኃ/የተ/የግል /ማኅበር በዚህ የክስ መዝገብ የቀረበባቸው ከባድ የሙስና ወንጀል ክስን በተመለከተ ብቻ በመሆኑና ክሱ የተቋረጠ ስለሆነ 9ኛ ተከሣሽን (አቶ ይልቃል የኔሰው) በተመለከተ የጋዜጣ ጥሪ እንዲደረግ የተሰጠው ትዕዛዝ እንዲሁም 10ኛ ተከሣሽን (የኛ ፔትሮሊየም) በተመለከተ ፖሊስ በአድራሻቸው አፈላልጎ እንዲያቀርበው የተሰጠው ትዕዛዞች ቀሪ እንዲሆኑ ታዟል።
ዘገባው የሸገር ሬዲዮ ነው ።
የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የልደታ ምድብ 3ኛ የሙስና ጉዳዮች ወንጀል ችሎት "በገበያ ላይ የነዳጅ እጥረት እንዲከሰት አድርገዋል"የተባሉ የኢትዮጵያ ነዳጅና ኢነርጂ ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተርን ጨምሮ በ13 ተከሳሾች ላይ የተመሰረተውን የከባድ ሙስና ወንጀል ክስ የ5ቱ እንዲቋረጥ መደረጉን አስታውቋል፡፡
የክስ መቃወሚያ እንዲያቀርቡ ሰኔ 1 ቀን 2018 ዓ.ም ቀጠሮ ተይዞ የነበረ ሲሆን በችሎቱ የክስ መቃወሚያውና የአቃቢ ህግ መልስ ተነቦ የክስ ማሻሻያያ እንዲደረግና ባልቀረቡ ተከሳሾች በጋዜጣ እንዲጠሩ ፍ/ቤቱ አዝዞ ለሰኔ 18/ 2018 ዓ/ም ቀጠሮ ተሰጥቶ ነበር።
ይሁንና የ5ቱ ተከሳሾች ማለትም 1ኛ ተከሳሽ ዲቦራ ፉፋ ፣4ኛ ተከሳሽ ይላቅ አወቀ፣ 5ኛ ተከሳሽ አበላ ግዛው እንዲሁም ፖሊስ አፋልጉኝ አውጥቶባቸው የነበረው 9ኛ ተከሳሽ ይልቃል የኔሰው እና 10 ተከሳሽ የኛ ፔትሮሊየም ኀ/የ/ግ/ ማህበር ክሳቸው እንዲቋረጥ ተወስኗል፡፡
ክሱ የተቋረጠው፣ ፍትህ ሚኒስቴር ክሱ አንዲቋረጥ አቤቱታ በማቅቡ አንደሆነ ፍረድ ቤቱ ጠቅሷል፡፡
4ኛ ተከሣሽ አቶ ይላቅ እወቀ ይብለው እና 5ኛ ተከሣሽ አቶ አበላ ግዛው በሪ በዚህ የክስ መዝገብ የቀረበባቸው 3ኛ ክስን በተመለከተ ብቻ በመሆኑና ክሱ የተቋረጠ ስለሆነ የአዲስ አበባ የቂሊንጦ ማረሚያ ቤት ተከሳሾች በሌላ ወንጀል የማይፈለጉ መሆኑን በማረጋገጥ ከእስር እንዲለቃቸው የእስር መፍቻ ትዕዛዝ እንዲፃፍ ታዟል።
9ኛ ተከሣሽ ይልቃል የኔሰው ዘለቀ እና 10ኛ ተከሣሽ የኛ ፔትሮሊየም ኃ/የተ/የግል /ማኅበር በዚህ የክስ መዝገብ የቀረበባቸው ከባድ የሙስና ወንጀል ክስን በተመለከተ ብቻ በመሆኑና ክሱ የተቋረጠ ስለሆነ 9ኛ ተከሣሽን (አቶ ይልቃል የኔሰው) በተመለከተ የጋዜጣ ጥሪ እንዲደረግ የተሰጠው ትዕዛዝ እንዲሁም 10ኛ ተከሣሽን (የኛ ፔትሮሊየም) በተመለከተ ፖሊስ በአድራሻቸው አፈላልጎ እንዲያቀርበው የተሰጠው ትዕዛዞች ቀሪ እንዲሆኑ ታዟል።
ዘገባው የሸገር ሬዲዮ ነው ።
6 days ago
የአርባ ምንጭ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የተገልጋዮችን እንግልት ለማስቀረት…
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 2፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የአርባ ምንጭ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የመንግስት አገልግሎቶችን ለማግኘት የነበረውን እንግልት የሚያስቀር ነው አሉ የከተማዋ ነዋሪዎች፡፡
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ በዛሬው ዕለት የአርባ ምንጭ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን መርቀው ለአገልግሎት ክፍት አድርገዋል።
የከተማዋ ነዋሪዎች ለፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን እንደገለጹት፥ ቀደም ሲል የመንግስት አገልግሎቶችን ለማግኘት ወደተለያዩ ቢሮዎች በመመላለስ ለከፍተኛ እንግልትና ለገንዘብ ብክነት ይዳረጉ ነበር።
ሁሉንም የመንግስት አገልግሎቶች በአንድ ጣራ ስር በአጭር ጊዜ በተቀላጠፈ ሁኔታ ለማግኘት የሚያስችለው የአንድ ማዕከል አገልግሎቱ በመጀመሩ መደሰታቸውን ገልጸዋል፡፡
ማዕከሉ በተለይም የንግድ ፈቃድ ለማውጣትና ተያያዥ ሂደቶችን ለማስፈጸም ይወስድ የነበረውን ረጅም ቀጠሮና ቢሮክራሲ የሚያቃልል ነው ብለዋል፡፡
ይህ አይነቱ አሰራር ለአካባቢው የንግድ እንቅስቃሴ መነቃቃትና ለኢንቨስትመንት ፍሰት ምቹ ሁኔታ ይፈጥራል ነው ያሉት፡፡
በቴክኖሎጂ የተደገፈው ይህ አዲስ አሰራር የህዝብን አመኔታ ከመጨመሩም በላይ ሙስናና አድሏዊነትን እንደሚያስቀር ተገልጿል፡፡
በመለሰ ታደለ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 2፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የአርባ ምንጭ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የመንግስት አገልግሎቶችን ለማግኘት የነበረውን እንግልት የሚያስቀር ነው አሉ የከተማዋ ነዋሪዎች፡፡
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ በዛሬው ዕለት የአርባ ምንጭ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን መርቀው ለአገልግሎት ክፍት አድርገዋል።
የከተማዋ ነዋሪዎች ለፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን እንደገለጹት፥ ቀደም ሲል የመንግስት አገልግሎቶችን ለማግኘት ወደተለያዩ ቢሮዎች በመመላለስ ለከፍተኛ እንግልትና ለገንዘብ ብክነት ይዳረጉ ነበር።
ሁሉንም የመንግስት አገልግሎቶች በአንድ ጣራ ስር በአጭር ጊዜ በተቀላጠፈ ሁኔታ ለማግኘት የሚያስችለው የአንድ ማዕከል አገልግሎቱ በመጀመሩ መደሰታቸውን ገልጸዋል፡፡
ማዕከሉ በተለይም የንግድ ፈቃድ ለማውጣትና ተያያዥ ሂደቶችን ለማስፈጸም ይወስድ የነበረውን ረጅም ቀጠሮና ቢሮክራሲ የሚያቃልል ነው ብለዋል፡፡
ይህ አይነቱ አሰራር ለአካባቢው የንግድ እንቅስቃሴ መነቃቃትና ለኢንቨስትመንት ፍሰት ምቹ ሁኔታ ይፈጥራል ነው ያሉት፡፡
በቴክኖሎጂ የተደገፈው ይህ አዲስ አሰራር የህዝብን አመኔታ ከመጨመሩም በላይ ሙስናና አድሏዊነትን እንደሚያስቀር ተገልጿል፡፡
በመለሰ ታደለ
7 days ago
“ወ/ሮ በረከት ወርቁን ጨምሮ ሌሎች ተከሳሾች ለችሎት እንዲቀርቡ የጋዜጣ ጥሪ እንዲወጣ ታዘዘ።”
ፖሊስ የሙስና ወንጀል ተከሰው በፖሊስ የፍለጋ ዝርዝር ውስጥ የተካተቱትን ወ/ሮ በረከት ወርቁን ጨምሮ አራት ግለሰቦችን ፖሊስ ለፍርድ ቤት ማቅረብ አልቻለም።
ጉዳዩን የተመለከተው የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የልደታ ምድብ 3ኛ የሙስና ወንጀል ችሎት ሲሆን፣ በ13 ተከሳሾች ላይ የተመሰረተውን ክስ መርምሯል።
በዚህ መዝገብ ውስጥ የኢትዮጵያ ነዳጅና ኢነርጂ ባለስልጣን እና የኢትዮጵያ ነዳጅ አቅራቢ ድርጅት ከፍተኛ ኃላፊዎችም ተካተዋል።
አቃቤ ህግ ተከሳሾቹ ስልጣናቸውን ከህግ ውጭ በመጠቀምና የመንግስት ሥራን ተገቢ ባልሆነ መንገድ በመምራት ጉዳት አድርሰዋል በሚል ክስ አቅርቧል።
ለዛሬ ተይዞ በነበረው ችሎት ከ6ኛ እስከ 10ኛ ተራ ቁጥር የተመዘገቡ ተከሳሾች ባለመገኘታቸው ሂደቱ ተራዝሟል። ፍርድ ቤቱም እነዚህ ግለሰቦች በጋዜጣ ጥሪ እንዲጠሩ ትዕዛዝ ሰጥቷል።
በተለይ ወ/ሮ በረከት ወርቁ ከሀገር ውጭ መገኘታቸው በማህበራዊ ሚዲያ በሚታዩ መረጃዎች መጠቆሙን ተከትሎ፣ ጥሪው በአዲስ ዘመን እና በኢትዮጵያን ሄራልድ ጋዜጦች እንዲታተም ተወስኗል።
ችሎቱ አቃቤ ህግ ክሱን አሻሽሎ እንዲያቀርብ በማዘዝ፣ የጉዳዩን ቀጣይ ሂደት ለመከታተል ለሰኔ 18 ቀን 2018 ዓ.ም ቀጠሮ ሰጥቷል።
Via ሸገር ኤፍኤም
Seledadotio
Seledadotio
ፖሊስ የሙስና ወንጀል ተከሰው በፖሊስ የፍለጋ ዝርዝር ውስጥ የተካተቱትን ወ/ሮ በረከት ወርቁን ጨምሮ አራት ግለሰቦችን ፖሊስ ለፍርድ ቤት ማቅረብ አልቻለም።
ጉዳዩን የተመለከተው የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የልደታ ምድብ 3ኛ የሙስና ወንጀል ችሎት ሲሆን፣ በ13 ተከሳሾች ላይ የተመሰረተውን ክስ መርምሯል።
በዚህ መዝገብ ውስጥ የኢትዮጵያ ነዳጅና ኢነርጂ ባለስልጣን እና የኢትዮጵያ ነዳጅ አቅራቢ ድርጅት ከፍተኛ ኃላፊዎችም ተካተዋል።
አቃቤ ህግ ተከሳሾቹ ስልጣናቸውን ከህግ ውጭ በመጠቀምና የመንግስት ሥራን ተገቢ ባልሆነ መንገድ በመምራት ጉዳት አድርሰዋል በሚል ክስ አቅርቧል።
ለዛሬ ተይዞ በነበረው ችሎት ከ6ኛ እስከ 10ኛ ተራ ቁጥር የተመዘገቡ ተከሳሾች ባለመገኘታቸው ሂደቱ ተራዝሟል። ፍርድ ቤቱም እነዚህ ግለሰቦች በጋዜጣ ጥሪ እንዲጠሩ ትዕዛዝ ሰጥቷል።
በተለይ ወ/ሮ በረከት ወርቁ ከሀገር ውጭ መገኘታቸው በማህበራዊ ሚዲያ በሚታዩ መረጃዎች መጠቆሙን ተከትሎ፣ ጥሪው በአዲስ ዘመን እና በኢትዮጵያን ሄራልድ ጋዜጦች እንዲታተም ተወስኗል።
ችሎቱ አቃቤ ህግ ክሱን አሻሽሎ እንዲያቀርብ በማዘዝ፣ የጉዳዩን ቀጣይ ሂደት ለመከታተል ለሰኔ 18 ቀን 2018 ዓ.ም ቀጠሮ ሰጥቷል።
Via ሸገር ኤፍኤም
Seledadotio
Seledadotio
7 days ago
ሰላም….ደህና አመሻችሁ?
ወደፊት ሊመጡ የሚችሉ ክስተቶችን እንተንብይ፡፡ እድሎችን እና ፈተናዎችን እንደ ሀገር ቀድመን እንረዳ፤ ሀገር ለማዳንና ለመገንባት ዛሬ እንዘጋጅ፡፡
ይህ እሳቤ እንደ ማህበረሰብ ካለፈው ተምረን፣ የዛሬን ተጨባጭ ሁኔታ አገናዝበን፣ ዘላቂ የነገን ህይወት እንድንገነባ ያስችለናል፡፡
ሀገራችን በትውልድ ቅብብሎሽ እኛ ጋር ደርሳለች፡፡ አሁን እኛ አደራ ተሸካሚዎች ነን፡፡
ከትናንቱ ትውልድ ሀገር የሚያሻግሩና የሚያሰባስቡንን ትርክቶች እንውረስ፡፡
ለጊዜያዊ ጥቅም ሳይሆን፣ ለነገው ትውልድና ለዘላቄታው እናስብ፡፡
በየዘመናቱ ሀገር ለማሻገር ዘላቂ ተቋማትን የመገንባት ትልሞች ነበሩ፡፡ ነገር ግን በውጭ ጫና እና በውስጥ ችግሮች የተነሳ እየጎተቱን ጠንካራ ማህበራዊ እና ህጋዊ ሥርዓቶችን መዘርጋት ተስኖን እስከ ዛሬ የቤት ሥራ ሆኖብን እየታገልን እንገኛለን፡፡
ይህ ደግሞ በየጊዜው ለሚመጡ ፈተናዎች ጊዜያዊ መፍትሄ ላይ እንድናተኩር እና ቀልባችንን ሰብሰብ አድርገን ሀገረ መንግሥት ግንባታ ላይ እንዳናደርግ አድርጎናል፡፡
በሌላ መልኩ ድህነታችን ስለ ነገ ከማሰብ ይልቅ ለዕለት ጉሮሯችን ብቻ እንድንጨነቅ ሲያደርገን ቆይቷል፡፡ ይህ ደግሞ ተደጋጋሚ ፖለቲካዊ እና ኢኮኖሚያዊ ቀውሶችን እያስተናገድን በየጊዜው አለመረጋጋት ውስጥ እንድንቆይ አስገድዶናል፡፡
እናማ አሁን ያ ጊዜ ሊያልፍ እና ልንነቃ ይገባናል!
ሀገራችንን መጠበቅ የእኛ የአሁኖቹ ትውልድ ድርሻ ነውና፡፡ አንድነታችንን፣ ሰላማችንን፣ ሉዓላዊነታችንን እና ደህንነታችንን የማስከበር ኃላፊነት አለብን፡፡ እነዚህን ማስከበር የፀጥታው አካል ስራ ብቻ ሳይሆን፣ የእኛ የዜጎች የእያንዳንዳችን የዕለት ተዕለት ተግባር እና ግዴታ መሆን አለበት፡፡ በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ተሳትፏችንን እንዳሳየነው ሁሉ፣ በሀገራችን ጉዳዮች በንቃት ስንሳተፍ ኢትዮጵያ ውስጣዊና ውጫዊ አደጋዎችን በቀላሉ መቋቋም ትችላለች።
ታዲያ እኛ እንደ ህዝብ ምን እናድርግ?
• ሀገራችንን እንጠብቅ!
ሀገር መጠበቅ የመንግሥት የሥራ ድርሻ ብቻ አይደለም፡፡ ለደህንነታችን ዘብ እንቁም፡፡ የአካባቢያችንን ሰላም በጋራ መጠበቅ እና አጠራጣሪ ድርጊቶችን ለህግ አስከባሪዎች በፍጥነት ማሳወቅ ይገባናል፡፡ ይህ የዜግነት ግዴታችንም ነው፡፡
• አንድነታችንን እናጠናክር!
ለከፋፋይ አስተሳሰቦች ጆሮ አንስጥ፡፡ ማህበራዊ ትስስራችንን የሚያላሉ የጥላቻ ንግግሮችን እና የህዝብ ለህዝብ ግጭቶችን መከላከል አለብን። አንዳችን ለሌላችን ጋሻ ነን፡፡ የተለየ አስተሳሰብ፣ ብሔር እና ሃይማኖት ሊኖረን ይችላል፡፡ ይህ ውበት እንጂ የሚያራርቅ ጉዳይ አይደለም፡፡ በመከባበር ለመኖር፣ የሀገርን ሰላም የሚነሱ ዋልታ ረገጥ ትርክቶችን እንከላከል፤ ማህበራዊ አንድነታችንን እናረጋግጥ፡፡ ያኔ ጠላቶቻችንም መግቢያ ቀዳዳ ያጣሉ፤ እኛም ሰላም እንሆናለን፡፡
• ብልሹ አሰራሮችንና ሙስናን እንዋጋ!
በየመስካችን በታማኝነት እንሥራ! እኛም ህጋዊ አሰራሮችን ብቻ እንከተል፡፡ ግብራችንንም በታማኝነት እንክፈል፡፡ ህግን አክብረን እናስከብር፡፡
• በራሳችን ምርት እንኩራ!
የሀገር ውስጥ ምርቶችን በመጠቀም እና ኮንትሮባንድን በመከላከል የሀገር ኢኮኖሚን ከውድቀት እንጠብቅ።
• የህዝብ መሠረተ ልማቶችን ከውድመት እንከላከል፡፡
የልማት ተቋማትን እንንከባከብ፡፡ ዛሬ የእኛ ናቸው፣ እንጠቀምባቸዋለን፡፡ ነገ ደግሞ ለቀጣዩ ትውልድ ይሻገራሉ፡፡ ለቀጣዩ ትውልድ የሚተርፍ ወረት እናቆይ፡፡
ኑ፤ ሀገር እንሥራ!
ወደፊት ሊመጡ የሚችሉ ክስተቶችን እንተንብይ፡፡ እድሎችን እና ፈተናዎችን እንደ ሀገር ቀድመን እንረዳ፤ ሀገር ለማዳንና ለመገንባት ዛሬ እንዘጋጅ፡፡
ይህ እሳቤ እንደ ማህበረሰብ ካለፈው ተምረን፣ የዛሬን ተጨባጭ ሁኔታ አገናዝበን፣ ዘላቂ የነገን ህይወት እንድንገነባ ያስችለናል፡፡
ሀገራችን በትውልድ ቅብብሎሽ እኛ ጋር ደርሳለች፡፡ አሁን እኛ አደራ ተሸካሚዎች ነን፡፡
ከትናንቱ ትውልድ ሀገር የሚያሻግሩና የሚያሰባስቡንን ትርክቶች እንውረስ፡፡
ለጊዜያዊ ጥቅም ሳይሆን፣ ለነገው ትውልድና ለዘላቄታው እናስብ፡፡
በየዘመናቱ ሀገር ለማሻገር ዘላቂ ተቋማትን የመገንባት ትልሞች ነበሩ፡፡ ነገር ግን በውጭ ጫና እና በውስጥ ችግሮች የተነሳ እየጎተቱን ጠንካራ ማህበራዊ እና ህጋዊ ሥርዓቶችን መዘርጋት ተስኖን እስከ ዛሬ የቤት ሥራ ሆኖብን እየታገልን እንገኛለን፡፡
ይህ ደግሞ በየጊዜው ለሚመጡ ፈተናዎች ጊዜያዊ መፍትሄ ላይ እንድናተኩር እና ቀልባችንን ሰብሰብ አድርገን ሀገረ መንግሥት ግንባታ ላይ እንዳናደርግ አድርጎናል፡፡
በሌላ መልኩ ድህነታችን ስለ ነገ ከማሰብ ይልቅ ለዕለት ጉሮሯችን ብቻ እንድንጨነቅ ሲያደርገን ቆይቷል፡፡ ይህ ደግሞ ተደጋጋሚ ፖለቲካዊ እና ኢኮኖሚያዊ ቀውሶችን እያስተናገድን በየጊዜው አለመረጋጋት ውስጥ እንድንቆይ አስገድዶናል፡፡
እናማ አሁን ያ ጊዜ ሊያልፍ እና ልንነቃ ይገባናል!
ሀገራችንን መጠበቅ የእኛ የአሁኖቹ ትውልድ ድርሻ ነውና፡፡ አንድነታችንን፣ ሰላማችንን፣ ሉዓላዊነታችንን እና ደህንነታችንን የማስከበር ኃላፊነት አለብን፡፡ እነዚህን ማስከበር የፀጥታው አካል ስራ ብቻ ሳይሆን፣ የእኛ የዜጎች የእያንዳንዳችን የዕለት ተዕለት ተግባር እና ግዴታ መሆን አለበት፡፡ በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ተሳትፏችንን እንዳሳየነው ሁሉ፣ በሀገራችን ጉዳዮች በንቃት ስንሳተፍ ኢትዮጵያ ውስጣዊና ውጫዊ አደጋዎችን በቀላሉ መቋቋም ትችላለች።
ታዲያ እኛ እንደ ህዝብ ምን እናድርግ?
• ሀገራችንን እንጠብቅ!
ሀገር መጠበቅ የመንግሥት የሥራ ድርሻ ብቻ አይደለም፡፡ ለደህንነታችን ዘብ እንቁም፡፡ የአካባቢያችንን ሰላም በጋራ መጠበቅ እና አጠራጣሪ ድርጊቶችን ለህግ አስከባሪዎች በፍጥነት ማሳወቅ ይገባናል፡፡ ይህ የዜግነት ግዴታችንም ነው፡፡
• አንድነታችንን እናጠናክር!
ለከፋፋይ አስተሳሰቦች ጆሮ አንስጥ፡፡ ማህበራዊ ትስስራችንን የሚያላሉ የጥላቻ ንግግሮችን እና የህዝብ ለህዝብ ግጭቶችን መከላከል አለብን። አንዳችን ለሌላችን ጋሻ ነን፡፡ የተለየ አስተሳሰብ፣ ብሔር እና ሃይማኖት ሊኖረን ይችላል፡፡ ይህ ውበት እንጂ የሚያራርቅ ጉዳይ አይደለም፡፡ በመከባበር ለመኖር፣ የሀገርን ሰላም የሚነሱ ዋልታ ረገጥ ትርክቶችን እንከላከል፤ ማህበራዊ አንድነታችንን እናረጋግጥ፡፡ ያኔ ጠላቶቻችንም መግቢያ ቀዳዳ ያጣሉ፤ እኛም ሰላም እንሆናለን፡፡
• ብልሹ አሰራሮችንና ሙስናን እንዋጋ!
በየመስካችን በታማኝነት እንሥራ! እኛም ህጋዊ አሰራሮችን ብቻ እንከተል፡፡ ግብራችንንም በታማኝነት እንክፈል፡፡ ህግን አክብረን እናስከብር፡፡
• በራሳችን ምርት እንኩራ!
የሀገር ውስጥ ምርቶችን በመጠቀም እና ኮንትሮባንድን በመከላከል የሀገር ኢኮኖሚን ከውድቀት እንጠብቅ።
• የህዝብ መሠረተ ልማቶችን ከውድመት እንከላከል፡፡
የልማት ተቋማትን እንንከባከብ፡፡ ዛሬ የእኛ ናቸው፣ እንጠቀምባቸዋለን፡፡ ነገ ደግሞ ለቀጣዩ ትውልድ ይሻገራሉ፡፡ ለቀጣዩ ትውልድ የሚተርፍ ወረት እናቆይ፡፡
ኑ፤ ሀገር እንሥራ!
7 days ago
በከባድ ሙስና የተከሰሱትን ወ/ሮ በረከት ወርቁን ጨምሮ 4 ተከሳሾችን፤ ፖሊስ ፍርድ ቤት ማቅረብ ሳይችል ቀረ፡፡
በከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመስርቶባቸው በፖሊስ የ'ይፈለጋሉ" ማስታወቂያ የወጣባቸው ወ/ሮ በረከት ወርቁን ጨምሮ አራት ተከሳሾን ፖሊስ በዛሬ ፍርድ ቤት እንዲያቀርብ ታዞ ነበር።
ፍርድ ቤቱ ተከሳሾቹ በጋዜጣ ጥሪ ተደርጎላቸው እንዲቀርቡ በማዘዝ ለሰኔ 18 ቀን 2018 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል።
የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የልደታ ምድብ 3ኛ የሙስና ጉዳዮች ወንጀል ችሎት፤ "በገበያ ላይ የነዳጅ እጥረት እንዲከሰት አድርገዋል" የተባሉ የኢትዮጵያ ነዳጅና ኢነርጂ ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተርን እና የኢትዮጵያ ነዳጅ አቅራቢ ድርጅት ዋና ዳይሬክተርን ጨምሮ በ13 ግለሰቦች ላይ የተመሰረተውን የከባድ ሙስና ወንጀል ክስ፣ የክስ መቃወሚያ እና የአቃቤ ህግን ምላሽ ዛሬ መርምሯል።
የፌደራል አቃቤ ህግ ተከሳሾቹን በዋና ወንጀል አድራጊነት እና በልዩ ተካፋይነት፤ ስልጣንን ያለአግባብ በመገልገልና የመንግስትን ስራ በማይመች አኳኋን በመምራት ወንጀል ከሷቸዋል።
ችሎቱ የተከሳሾችን የክስ መቃወሚያ እና የአቃቤ ህግን ምላሽ ለመስማት ለዛሬ ሰኔ 1 ቀን 2018 ዓ.ም ቀጠሮ ይዞ የነበረ ቢሆንም፣ በክስ መዝገቡ ከ6ኛ እስከ 10ኛ ተራ ቁጥር ላይ የተጠቀሱት ተከሳሾች ሳይገኙ ቀርተዋል።
ችሎት ያልተገኙት ተጠርጣሪዎች በከባድ የሙስና ወንጀል ተፈልገው ማግኘት ባለመቻሉ፣ ፖሊስ ቀደም ሲል የ"ይፈለጋሉ" ማስታወቂያ አውጥቶባቸው እንደነበር ይታወሳል።
ዛሬ በዋለው ችሎት የቀረበውን የክስ መቃወሚያ እና የአቃቤ ህግን ምላሽ የመረመረው ፍርድ ቤቱ፤ አቃቤ ህግ ክሱን ለይቶ (አሻሽሎ) እንዲያቀርብም አዝዟል።
በተጨማሪም በችሎቱ ያልተገኙት ተከሳሾች በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ጥሪ እንዲደረግላቸው ትዕዛዝ አስተላልፏል።
በመዝገቡ 7ኛ ተከሳሽ የሆኑት ወ/ሮ በረከት ወርቁ ከሀገር መውጣታቸው በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያዎች በሚያደርጉት ንግግር በመረጋገጡ፣ አቃቤ ህግ ለእሳቸው ጥሪው በአዲስ ዘመን እና በኢትዮጵያን ሄራልድ ጋዜጦች ጭምር እንዲያወጣ ባቀረበው ማሳሰቢያ መሰረት ፍርድ ቤቱ ትዕዛዝ ሰጥቷል።
ችሎቱ የተሻሻለውን ክስ ለመመልከት እና የጥሪውን ሂደት ለመከታተል ለሰኔ 18 ቀን 2018 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል።
ዘገባው የሸገር ሬዲዮ ነው።
በከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመስርቶባቸው በፖሊስ የ'ይፈለጋሉ" ማስታወቂያ የወጣባቸው ወ/ሮ በረከት ወርቁን ጨምሮ አራት ተከሳሾን ፖሊስ በዛሬ ፍርድ ቤት እንዲያቀርብ ታዞ ነበር።
ፍርድ ቤቱ ተከሳሾቹ በጋዜጣ ጥሪ ተደርጎላቸው እንዲቀርቡ በማዘዝ ለሰኔ 18 ቀን 2018 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል።
የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የልደታ ምድብ 3ኛ የሙስና ጉዳዮች ወንጀል ችሎት፤ "በገበያ ላይ የነዳጅ እጥረት እንዲከሰት አድርገዋል" የተባሉ የኢትዮጵያ ነዳጅና ኢነርጂ ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተርን እና የኢትዮጵያ ነዳጅ አቅራቢ ድርጅት ዋና ዳይሬክተርን ጨምሮ በ13 ግለሰቦች ላይ የተመሰረተውን የከባድ ሙስና ወንጀል ክስ፣ የክስ መቃወሚያ እና የአቃቤ ህግን ምላሽ ዛሬ መርምሯል።
የፌደራል አቃቤ ህግ ተከሳሾቹን በዋና ወንጀል አድራጊነት እና በልዩ ተካፋይነት፤ ስልጣንን ያለአግባብ በመገልገልና የመንግስትን ስራ በማይመች አኳኋን በመምራት ወንጀል ከሷቸዋል።
ችሎቱ የተከሳሾችን የክስ መቃወሚያ እና የአቃቤ ህግን ምላሽ ለመስማት ለዛሬ ሰኔ 1 ቀን 2018 ዓ.ም ቀጠሮ ይዞ የነበረ ቢሆንም፣ በክስ መዝገቡ ከ6ኛ እስከ 10ኛ ተራ ቁጥር ላይ የተጠቀሱት ተከሳሾች ሳይገኙ ቀርተዋል።
ችሎት ያልተገኙት ተጠርጣሪዎች በከባድ የሙስና ወንጀል ተፈልገው ማግኘት ባለመቻሉ፣ ፖሊስ ቀደም ሲል የ"ይፈለጋሉ" ማስታወቂያ አውጥቶባቸው እንደነበር ይታወሳል።
ዛሬ በዋለው ችሎት የቀረበውን የክስ መቃወሚያ እና የአቃቤ ህግን ምላሽ የመረመረው ፍርድ ቤቱ፤ አቃቤ ህግ ክሱን ለይቶ (አሻሽሎ) እንዲያቀርብም አዝዟል።
በተጨማሪም በችሎቱ ያልተገኙት ተከሳሾች በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ጥሪ እንዲደረግላቸው ትዕዛዝ አስተላልፏል።
በመዝገቡ 7ኛ ተከሳሽ የሆኑት ወ/ሮ በረከት ወርቁ ከሀገር መውጣታቸው በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያዎች በሚያደርጉት ንግግር በመረጋገጡ፣ አቃቤ ህግ ለእሳቸው ጥሪው በአዲስ ዘመን እና በኢትዮጵያን ሄራልድ ጋዜጦች ጭምር እንዲያወጣ ባቀረበው ማሳሰቢያ መሰረት ፍርድ ቤቱ ትዕዛዝ ሰጥቷል።
ችሎቱ የተሻሻለውን ክስ ለመመልከት እና የጥሪውን ሂደት ለመከታተል ለሰኔ 18 ቀን 2018 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል።
ዘገባው የሸገር ሬዲዮ ነው።
Sponsored by
Surafel
9 days ago
"ኢትዮጵያ በቅኝ ግዛት ሳትገዛም ድሃ ናት፤ በፈረንሳይ የተገዛችው ቬትናም ግን ዛሬ በልጽጋለች"
📌ቁጣን የቀሰቀሰው የ x ገጽ ልጥፍ
#ethiopia | የዓለማችን ቢሊየነር ኢሎን ማስክ እና ሴኔጋላዊቷ ስራ ፈጣሪ ማጋቴ ዋድ ሰሞኑን በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ያራገቡት አወዛጋቢ ትርክት፣ በአፍሪካውያን እና በታሪክ ምሁራን ዘንድ ትልቅ ቁጣን ቀስቅሷል። ማጋቴ ዋድ "ኢትዮጵያ በቅኝ ግዛት ሳትገዛም ድሃ ናት፤ በፈረንሳይ የተገዛችው ቬትናም ግን ዛሬ በልጽጋለች" በማለት የቅኝ ግዛትን አስከፊ ታሪክ ለማቃለል የሞከረች ሲሆን፣ ኢሎን ማስክም ለዚህ ታሪካዊ ስህተት አጋርነቱን አሳይቷል። ይሁን እንጂ ይህ መከራከሪያ ሆን ተብሎ የተመረጡ መረጃዎችን ብቻ በመጠቀም የተነዛ፣ ሚዛናዊነት የጎደለው እና የጥቁር ሕዝቦችን የነጻነት ተምሳሌት የሆነችውን ኢትዮጵያን ክብረ-ታሪክ ያጣጣለ ትልቅ የታሪክ ክህደት ነው።
የማጋቴ ዋድ ትልቁ የታሪክ ስህተት እና ማጭበርበር የሚጋለጠው፣ በእሷው አመክንዮ ውስጥ ያሉትን ግልጽ ተቃርኖዎች ስንመለከት ነው። ቬትናምን እንደ ብቸኛ የስኬት ማሳያ አድርጋ ስታቀርብ፣ ልክ እንደ ቬትናም በፈረንሳይ ቅኝ ግዛት ስር የነበሩ ነገር ግን ዛሬም ድረስ ከኢትዮጵያ በታች በሆነ የድህነት አዘቅት ውስጥ የሚገኙትን በርካታ የአፍሪካ ሀገራት ሆን ብላ ዘንግታዋለች።
ኒጀር፣ የመካከለኛው አፍሪካ ሪፐብሊክ፣ ቻድ፣ ማዳጋስካር እና ቡርኪና ፋሶን የመሳሰሉ ሀገራት ለዘመናት በፈረንሳይ ቅኝ ግዛት ስር ቆይተዋል። ይሁን እንጂ ዛሬ ላይ በነፍስ ወከፍ ገቢያቸውም (GDP per capita) ሆነ በሰብዓዊ ልማት ጠቋሚያቸው (HDI) ከኢትዮጵያ በእጅጉ ያነሱ እና በዓለም መጨረሻ ላይ የሚገኙ ናቸው። ቅኝ ግዛት የብልጽግና እና የሰለጠነ መዋቅር ምንጭ ቢሆን ኖሮ፣ እነዚህ የፈረንሳይ ቅኝ ግዛቶች ዛሬ ለምን የዓለም አቀፍ የድህነት መለኪያ ሆኑ? አሁንም ድረስ ፈረንሳይ በዘረጋችው የኒዮ-ኮሎኒያሊዝም መዋቅር (በተለይም በCFA ፍራንክ የገንዘብ ሥርዓት) የራሳቸውን ሀብት ማስተዳደር አቅቷቸው በከፍተኛ ፖለቲካዊ እና ኢኮኖሚያዊ ቀውስ ውስጥ ይገኛሉ። ይህ ሐቅ "ቅኝ ግዛት የድህነት ምክንያት አይደለም" የሚለውን የማጋቴን መከራከሪያ ከመሠረቱ የሚያፈርስ ነው።
ቬትናም ዛሬ ላለችበት የኢኮኖሚ ከፍታ የበቃችው በፈረንሳይ ቅኝ ግዛት በረከት ሳይሆን፣ እንዲያውም የፈረንሳይን እና የአሜሪካን አውዳሚ ጦርነቶች በከፍተኛ መስዋዕትነት አሸንፋ ከወጣች በኋላ ነው። ሀገሪቱ ከጦርነቱ ፍርስራሽ ተነስታ ያደገችው በ1986 (እ.ኤ.አ.) ተግባራዊ ባደረገችው 'ዶይ ሞይ' (Doi Moi) የተሰኘው የውስጥ የኢኮኖሚ ማሻሻያ እና የእስያ ቀጠና በፈጠረላት ምቹ የንግድ ትስስር እንጂ የቅኝ ገዥዎች ትሩፋት አይደለም። የቬትናምን የላብ እና የደም ውጤት ለቅኝ ገዥዎች ታሪክ ማሳመሪያ ማድረግ ፍጹም ስህተት ነው።
ማጋቴ ዋድ የኢትዮጵያን ነጻነት ከድህነት ጋር አያይዛ ለማቅረብ መሞከሯ፣ የሀገሪቱን ታላቅነት እና የገጠማትን ውስብስብ ፈተና ካለመረዳት የመነጨ ነው። ኢትዮጵያ በአፍሪካ ምድር የነጭ የበላይነትን በአድዋ ተራሮች ላይ በመቅበር፣ ለመላው ጥቁር ሕዝብ የነጻነት እና የፓን-አፍሪካኒዝም ፋና ወጊ የሆነች ታላቅ ሀገር ናት። በቅኝ አለመገዛቷ የኩራቷ እንጂ የድህነቷ መንስኤ አይደለም።
የኢትዮጵያ ዘመናዊ የኢኮኖሚ ፈተናዎች የመነጩት ከነጻነቷ ሳይሆን፣ በዙሪያዋ ከነበሩት የቅኝ ገዥ ኃይሎች ሴራ እና ከውስጣዊ ፖለቲካዊ ውጣ ውረዶች ነው። መላው አፍሪካ በቅኝ ግዛት ሲከፋፈል፣ ነጻዋ ኢትዮጵያ በቅኝ ገዥዎች ተከባ የባህር በር እንድታጣ እና ከዓለም አቀፍ ንግድ እንድትገለል ተደርጋለች። በቅርቡ ታሪክም በቀዝቃዛው ጦርነት የጂኦፖለቲካዊ ሽኩቻ ሰለባ በመሆን፣ እንዲሁም ደርግ በተከተለው አውዳሚ የማርክሲስት የኢኮኖሚ ሥርዓት እና በተራዘሙ የእርስ በርስ ጦርነቶች ምክንያት ኢኮኖሚዋ ክፉኛ ተጎድቷል። እነዚህ ሁሉ ፈተናዎች ቢኖሩም፣ ኢትዮጵያ የራሷን ቋንቋ፣ ባህል፣ የቀን አቆጣጠር እና ሀገራዊ ኩራት ጠብቃ ያቆየች፤ ዛሬም በአፍሪካ ቀንድ ትልቅ የኢኮኖሚ እና የፖለቲካ ተጽዕኖ ፈጣሪ መሆን የቻለች ሀገር ናት።
የአፍሪካን ወቅታዊ ችግሮች ለመፍታት ራስን መመርመር፣ ሙስናን መዋጋት እና የተሻለ አስተዳደር መገንባት አማራጭ የሌለው ጉዳይ ነው። ነገር ግን ይህንን ለማድረግ ሲባል የቅኝ ግዛትን አስከፊነት ማጠብ እና የኢትዮጵያን ደማቅ የነጻነት ታሪክ ማጠልሸት አይቻልም። ኢትዮጵያ ምንም እንኳን የኢኮኖሚ ፈተናዎች ቢኖሩባትም፣ የማንም ቅኝ ገዥ ሎሌ ሳትሆን የራሷን ዕድል በራሷ የወሰነች የአፍሪካ የቁርጥ ቀን ልጅ ናት። አህጉሪቱ ወደፊት መራመድ ያለባት የቅኝ ግዛትን ጠባሳ በማስተባበል ሳይሆን፣ እንደ ኢትዮጵያ ሁሉ የራስን ማንነት አጥብቆ በመያዝ እና ጠንካራ ኢኮኖሚን በነጻነት ላይ በመገንባት ሊሆን ይገባል።
#ዘሐበሻ
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
📌ቁጣን የቀሰቀሰው የ x ገጽ ልጥፍ
#ethiopia | የዓለማችን ቢሊየነር ኢሎን ማስክ እና ሴኔጋላዊቷ ስራ ፈጣሪ ማጋቴ ዋድ ሰሞኑን በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ያራገቡት አወዛጋቢ ትርክት፣ በአፍሪካውያን እና በታሪክ ምሁራን ዘንድ ትልቅ ቁጣን ቀስቅሷል። ማጋቴ ዋድ "ኢትዮጵያ በቅኝ ግዛት ሳትገዛም ድሃ ናት፤ በፈረንሳይ የተገዛችው ቬትናም ግን ዛሬ በልጽጋለች" በማለት የቅኝ ግዛትን አስከፊ ታሪክ ለማቃለል የሞከረች ሲሆን፣ ኢሎን ማስክም ለዚህ ታሪካዊ ስህተት አጋርነቱን አሳይቷል። ይሁን እንጂ ይህ መከራከሪያ ሆን ተብሎ የተመረጡ መረጃዎችን ብቻ በመጠቀም የተነዛ፣ ሚዛናዊነት የጎደለው እና የጥቁር ሕዝቦችን የነጻነት ተምሳሌት የሆነችውን ኢትዮጵያን ክብረ-ታሪክ ያጣጣለ ትልቅ የታሪክ ክህደት ነው።
የማጋቴ ዋድ ትልቁ የታሪክ ስህተት እና ማጭበርበር የሚጋለጠው፣ በእሷው አመክንዮ ውስጥ ያሉትን ግልጽ ተቃርኖዎች ስንመለከት ነው። ቬትናምን እንደ ብቸኛ የስኬት ማሳያ አድርጋ ስታቀርብ፣ ልክ እንደ ቬትናም በፈረንሳይ ቅኝ ግዛት ስር የነበሩ ነገር ግን ዛሬም ድረስ ከኢትዮጵያ በታች በሆነ የድህነት አዘቅት ውስጥ የሚገኙትን በርካታ የአፍሪካ ሀገራት ሆን ብላ ዘንግታዋለች።
ኒጀር፣ የመካከለኛው አፍሪካ ሪፐብሊክ፣ ቻድ፣ ማዳጋስካር እና ቡርኪና ፋሶን የመሳሰሉ ሀገራት ለዘመናት በፈረንሳይ ቅኝ ግዛት ስር ቆይተዋል። ይሁን እንጂ ዛሬ ላይ በነፍስ ወከፍ ገቢያቸውም (GDP per capita) ሆነ በሰብዓዊ ልማት ጠቋሚያቸው (HDI) ከኢትዮጵያ በእጅጉ ያነሱ እና በዓለም መጨረሻ ላይ የሚገኙ ናቸው። ቅኝ ግዛት የብልጽግና እና የሰለጠነ መዋቅር ምንጭ ቢሆን ኖሮ፣ እነዚህ የፈረንሳይ ቅኝ ግዛቶች ዛሬ ለምን የዓለም አቀፍ የድህነት መለኪያ ሆኑ? አሁንም ድረስ ፈረንሳይ በዘረጋችው የኒዮ-ኮሎኒያሊዝም መዋቅር (በተለይም በCFA ፍራንክ የገንዘብ ሥርዓት) የራሳቸውን ሀብት ማስተዳደር አቅቷቸው በከፍተኛ ፖለቲካዊ እና ኢኮኖሚያዊ ቀውስ ውስጥ ይገኛሉ። ይህ ሐቅ "ቅኝ ግዛት የድህነት ምክንያት አይደለም" የሚለውን የማጋቴን መከራከሪያ ከመሠረቱ የሚያፈርስ ነው።
ቬትናም ዛሬ ላለችበት የኢኮኖሚ ከፍታ የበቃችው በፈረንሳይ ቅኝ ግዛት በረከት ሳይሆን፣ እንዲያውም የፈረንሳይን እና የአሜሪካን አውዳሚ ጦርነቶች በከፍተኛ መስዋዕትነት አሸንፋ ከወጣች በኋላ ነው። ሀገሪቱ ከጦርነቱ ፍርስራሽ ተነስታ ያደገችው በ1986 (እ.ኤ.አ.) ተግባራዊ ባደረገችው 'ዶይ ሞይ' (Doi Moi) የተሰኘው የውስጥ የኢኮኖሚ ማሻሻያ እና የእስያ ቀጠና በፈጠረላት ምቹ የንግድ ትስስር እንጂ የቅኝ ገዥዎች ትሩፋት አይደለም። የቬትናምን የላብ እና የደም ውጤት ለቅኝ ገዥዎች ታሪክ ማሳመሪያ ማድረግ ፍጹም ስህተት ነው።
ማጋቴ ዋድ የኢትዮጵያን ነጻነት ከድህነት ጋር አያይዛ ለማቅረብ መሞከሯ፣ የሀገሪቱን ታላቅነት እና የገጠማትን ውስብስብ ፈተና ካለመረዳት የመነጨ ነው። ኢትዮጵያ በአፍሪካ ምድር የነጭ የበላይነትን በአድዋ ተራሮች ላይ በመቅበር፣ ለመላው ጥቁር ሕዝብ የነጻነት እና የፓን-አፍሪካኒዝም ፋና ወጊ የሆነች ታላቅ ሀገር ናት። በቅኝ አለመገዛቷ የኩራቷ እንጂ የድህነቷ መንስኤ አይደለም።
የኢትዮጵያ ዘመናዊ የኢኮኖሚ ፈተናዎች የመነጩት ከነጻነቷ ሳይሆን፣ በዙሪያዋ ከነበሩት የቅኝ ገዥ ኃይሎች ሴራ እና ከውስጣዊ ፖለቲካዊ ውጣ ውረዶች ነው። መላው አፍሪካ በቅኝ ግዛት ሲከፋፈል፣ ነጻዋ ኢትዮጵያ በቅኝ ገዥዎች ተከባ የባህር በር እንድታጣ እና ከዓለም አቀፍ ንግድ እንድትገለል ተደርጋለች። በቅርቡ ታሪክም በቀዝቃዛው ጦርነት የጂኦፖለቲካዊ ሽኩቻ ሰለባ በመሆን፣ እንዲሁም ደርግ በተከተለው አውዳሚ የማርክሲስት የኢኮኖሚ ሥርዓት እና በተራዘሙ የእርስ በርስ ጦርነቶች ምክንያት ኢኮኖሚዋ ክፉኛ ተጎድቷል። እነዚህ ሁሉ ፈተናዎች ቢኖሩም፣ ኢትዮጵያ የራሷን ቋንቋ፣ ባህል፣ የቀን አቆጣጠር እና ሀገራዊ ኩራት ጠብቃ ያቆየች፤ ዛሬም በአፍሪካ ቀንድ ትልቅ የኢኮኖሚ እና የፖለቲካ ተጽዕኖ ፈጣሪ መሆን የቻለች ሀገር ናት።
የአፍሪካን ወቅታዊ ችግሮች ለመፍታት ራስን መመርመር፣ ሙስናን መዋጋት እና የተሻለ አስተዳደር መገንባት አማራጭ የሌለው ጉዳይ ነው። ነገር ግን ይህንን ለማድረግ ሲባል የቅኝ ግዛትን አስከፊነት ማጠብ እና የኢትዮጵያን ደማቅ የነጻነት ታሪክ ማጠልሸት አይቻልም። ኢትዮጵያ ምንም እንኳን የኢኮኖሚ ፈተናዎች ቢኖሩባትም፣ የማንም ቅኝ ገዥ ሎሌ ሳትሆን የራሷን ዕድል በራሷ የወሰነች የአፍሪካ የቁርጥ ቀን ልጅ ናት። አህጉሪቱ ወደፊት መራመድ ያለባት የቅኝ ግዛትን ጠባሳ በማስተባበል ሳይሆን፣ እንደ ኢትዮጵያ ሁሉ የራስን ማንነት አጥብቆ በመያዝ እና ጠንካራ ኢኮኖሚን በነጻነት ላይ በመገንባት ሊሆን ይገባል።
#ዘሐበሻ
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
9 days ago
የዓለማችን ቢሊየነር ኢሎን ማስክ እና ሴኔጋላዊቷ ስራ ፈጣሪ ማጋቴ ዋድ ሰሞኑን በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ያራገቡት አወዛጋቢ ትርክት፣ በአፍሪካውያን እና በታሪክ ምሁራን ዘንድ ትልቅ ቁጣን ቀስቅሷል። ማጋቴ ዋድ "ኢትዮጵያ በቅኝ ግዛት ሳትገዛም ድሃ ናት፤ በፈረንሳይ የተገዛችው ቬትናም ግን ዛሬ በልጽጋለች" በማለት የቅኝ ግዛትን አስከፊ ታሪክ ለማቃለል የሞከረች ሲሆን፣ ኢሎን ማስክም ለዚህ ታሪካዊ ስህተት አጋርነቱን አሳይቷል። ይሁን እንጂ ይህ መከራከሪያ ሆን ተብሎ የተመረጡ መረጃዎችን ብቻ በመጠቀም የተነዛ፣ ሚዛናዊነት የጎደለው እና የጥቁር ሕዝቦችን የነጻነት ተምሳሌት የሆነችውን ኢትዮጵያን ክብረ-ታሪክ ያጣጣለ ትልቅ የታሪክ ክህደት ነው።
የማጋቴ ዋድ ትልቁ የታሪክ ስህተት እና ማጭበርበር የሚጋለጠው፣ በእሷው አመክንዮ ውስጥ ያሉትን ግልጽ ተቃርኖዎች ስንመለከት ነው። ቬትናምን እንደ ብቸኛ የስኬት ማሳያ አድርጋ ስታቀርብ፣ ልክ እንደ ቬትናም በፈረንሳይ ቅኝ ግዛት ስር የነበሩ ነገር ግን ዛሬም ድረስ ከኢትዮጵያ በታች በሆነ የድህነት አዘቅት ውስጥ የሚገኙትን በርካታ የአፍሪካ ሀገራት ሆን ብላ ዘንግታዋለች።
ኒጀር፣ የመካከለኛው አፍሪካ ሪፐብሊክ፣ ቻድ፣ ማዳጋስካር እና ቡርኪና ፋሶን የመሳሰሉ ሀገራት ለዘመናት በፈረንሳይ ቅኝ ግዛት ስር ቆይተዋል። ይሁን እንጂ ዛሬ ላይ በነፍስ ወከፍ ገቢያቸውም (GDP per capita) ሆነ በሰብዓዊ ልማት ጠቋሚያቸው (HDI) ከኢትዮጵያ በእጅጉ ያነሱ እና በዓለም መጨረሻ ላይ የሚገኙ ናቸው። ቅኝ ግዛት የብልጽግና እና የሰለጠነ መዋቅር ምንጭ ቢሆን ኖሮ፣ እነዚህ የፈረንሳይ ቅኝ ግዛቶች ዛሬ ለምን የዓለም አቀፍ የድህነት መለኪያ ሆኑ? አሁንም ድረስ ፈረንሳይ በዘረጋችው የኒዮ-ኮሎኒያሊዝም መዋቅር (በተለይም በCFA ፍራንክ የገንዘብ ሥርዓት) የራሳቸውን ሀብት ማስተዳደር አቅቷቸው በከፍተኛ ፖለቲካዊ እና ኢኮኖሚያዊ ቀውስ ውስጥ ይገኛሉ። ይህ ሐቅ "ቅኝ ግዛት የድህነት ምክንያት አይደለም" የሚለውን የማጋቴን መከራከሪያ ከመሠረቱ የሚያፈርስ ነው።
ቬትናም ዛሬ ላለችበት የኢኮኖሚ ከፍታ የበቃችው በፈረንሳይ ቅኝ ግዛት በረከት ሳይሆን፣ እንዲያውም የፈረንሳይን እና የአሜሪካን አውዳሚ ጦርነቶች በከፍተኛ መስዋዕትነት አሸንፋ ከወጣች በኋላ ነው። ሀገሪቱ ከጦርነቱ ፍርስራሽ ተነስታ ያደገችው በ1986 (እ.ኤ.አ.) ተግባራዊ ባደረገችው 'ዶይ ሞይ' (Doi Moi) የተሰኘው የውስጥ የኢኮኖሚ ማሻሻያ እና የእስያ ቀጠና በፈጠረላት ምቹ የንግድ ትስስር እንጂ የቅኝ ገዥዎች ትሩፋት አይደለም። የቬትናምን የላብ እና የደም ውጤት ለቅኝ ገዥዎች ታሪክ ማሳመሪያ ማድረግ ፍጹም ስህተት ነው።
ማጋቴ ዋድ የኢትዮጵያን ነጻነት ከድህነት ጋር አያይዛ ለማቅረብ መሞከሯ፣ የሀገሪቱን ታላቅነት እና የገጠማትን ውስብስብ ፈተና ካለመረዳት የመነጨ ነው። ኢትዮጵያ በአፍሪካ ምድር የነጭ የበላይነትን በአድዋ ተራሮች ላይ በመቅበር፣ ለመላው ጥቁር ሕዝብ የነጻነት እና የፓን-አፍሪካኒዝም ፋና ወጊ የሆነች ታላቅ ሀገር ናት። በቅኝ አለመገዛቷ የኩራቷ እንጂ የድህነቷ መንስኤ አይደለም።
የኢትዮጵያ ዘመናዊ የኢኮኖሚ ፈተናዎች የመነጩት ከነጻነቷ ሳይሆን፣ በዙሪያዋ ከነበሩት የቅኝ ገዥ ኃይሎች ሴራ እና ከውስጣዊ ፖለቲካዊ ውጣ ውረዶች ነው። მላው አፍሪካ በቅኝ ግዛት ሲከፋፈል፣ ነጻዋ ኢትዮጵያ በቅኝ ገዥዎች ተከባ የባህር በር እንድታጣ እና ከዓለም አቀፍ ንግድ እንድትገለል ተደርጋለች። በቅርቡ ታሪክም በቀዝቃዛው ጦርነት የጂኦፖለቲካዊ ሽኩቻ ሰለባ በመሆን፣ እንዲሁም ደርግ በተከተለው አውዳሚ የማርክሲስት የኢኮኖሚ ሥርዓት እና በተራዘሙ የእርስ በርስ ጦርነቶች ምክንያት ኢኮኖሚዋ ክፉኛ ተጎድቷል። እነዚህ ሁሉ ፈተናዎች ቢኖሩም፣ ኢትዮጵያ የራሷን ቋንቋ፣ ባህል፣ የቀን አቆጣጠር እና ሀገራዊ ኩራት ጠብቃ ያቆየች፤ ዛሬም በአፍሪካ ቀንድ ትልቅ የኢኮኖሚ እና የፖለቲካ ተጽዕኖ ፈጣሪ መሆን የቻለች ሀገር ናት።
የአፍሪካን ወቅታዊ ችግሮች ለመፍታት ራስን መመርመር፣ ሙስናን መዋጋት እና የተሻለ አስተዳደር መገንባት አማራጭ የሌለው ጉዳይ ነው። ነገር ግን ይህንን ለማድረግ ሲባል የቅኝ ግዛትን አስከፊነት ማጠብ እና የኢትዮጵያን ደማቅ የነጻነት ታሪክ ማጠልሸት አይቻልም። ኢትዮጵያ ምንም እንኳን የኢኮኖሚ ፈተናዎች ቢኖሩባትም፣ የማንም ቅኝ ገዥ ሎሌ ሳትሆን የራሷን ዕድል በራሷ የወሰነች የአፍሪካ የቁርጥ ቀን ልጅ ናት። አህጉሪቱ ወደፊት መራመድ ያለባት የቅኝ ግዛትን ጠባሳ በማስተባበል ሳይሆን፣ እንደ ኢትዮጵያ ሁሉ የራስን ማንነት አጥብቆ በመያዝ እና ጠንካራ ኢኮኖሚን በነጻነት ላይ በመገንባት ሊሆን ይገባል።
የማጋቴ ዋድ ትልቁ የታሪክ ስህተት እና ማጭበርበር የሚጋለጠው፣ በእሷው አመክንዮ ውስጥ ያሉትን ግልጽ ተቃርኖዎች ስንመለከት ነው። ቬትናምን እንደ ብቸኛ የስኬት ማሳያ አድርጋ ስታቀርብ፣ ልክ እንደ ቬትናም በፈረንሳይ ቅኝ ግዛት ስር የነበሩ ነገር ግን ዛሬም ድረስ ከኢትዮጵያ በታች በሆነ የድህነት አዘቅት ውስጥ የሚገኙትን በርካታ የአፍሪካ ሀገራት ሆን ብላ ዘንግታዋለች።
ኒጀር፣ የመካከለኛው አፍሪካ ሪፐብሊክ፣ ቻድ፣ ማዳጋስካር እና ቡርኪና ፋሶን የመሳሰሉ ሀገራት ለዘመናት በፈረንሳይ ቅኝ ግዛት ስር ቆይተዋል። ይሁን እንጂ ዛሬ ላይ በነፍስ ወከፍ ገቢያቸውም (GDP per capita) ሆነ በሰብዓዊ ልማት ጠቋሚያቸው (HDI) ከኢትዮጵያ በእጅጉ ያነሱ እና በዓለም መጨረሻ ላይ የሚገኙ ናቸው። ቅኝ ግዛት የብልጽግና እና የሰለጠነ መዋቅር ምንጭ ቢሆን ኖሮ፣ እነዚህ የፈረንሳይ ቅኝ ግዛቶች ዛሬ ለምን የዓለም አቀፍ የድህነት መለኪያ ሆኑ? አሁንም ድረስ ፈረንሳይ በዘረጋችው የኒዮ-ኮሎኒያሊዝም መዋቅር (በተለይም በCFA ፍራንክ የገንዘብ ሥርዓት) የራሳቸውን ሀብት ማስተዳደር አቅቷቸው በከፍተኛ ፖለቲካዊ እና ኢኮኖሚያዊ ቀውስ ውስጥ ይገኛሉ። ይህ ሐቅ "ቅኝ ግዛት የድህነት ምክንያት አይደለም" የሚለውን የማጋቴን መከራከሪያ ከመሠረቱ የሚያፈርስ ነው።
ቬትናም ዛሬ ላለችበት የኢኮኖሚ ከፍታ የበቃችው በፈረንሳይ ቅኝ ግዛት በረከት ሳይሆን፣ እንዲያውም የፈረንሳይን እና የአሜሪካን አውዳሚ ጦርነቶች በከፍተኛ መስዋዕትነት አሸንፋ ከወጣች በኋላ ነው። ሀገሪቱ ከጦርነቱ ፍርስራሽ ተነስታ ያደገችው በ1986 (እ.ኤ.አ.) ተግባራዊ ባደረገችው 'ዶይ ሞይ' (Doi Moi) የተሰኘው የውስጥ የኢኮኖሚ ማሻሻያ እና የእስያ ቀጠና በፈጠረላት ምቹ የንግድ ትስስር እንጂ የቅኝ ገዥዎች ትሩፋት አይደለም። የቬትናምን የላብ እና የደም ውጤት ለቅኝ ገዥዎች ታሪክ ማሳመሪያ ማድረግ ፍጹም ስህተት ነው።
ማጋቴ ዋድ የኢትዮጵያን ነጻነት ከድህነት ጋር አያይዛ ለማቅረብ መሞከሯ፣ የሀገሪቱን ታላቅነት እና የገጠማትን ውስብስብ ፈተና ካለመረዳት የመነጨ ነው። ኢትዮጵያ በአፍሪካ ምድር የነጭ የበላይነትን በአድዋ ተራሮች ላይ በመቅበር፣ ለመላው ጥቁር ሕዝብ የነጻነት እና የፓን-አፍሪካኒዝም ፋና ወጊ የሆነች ታላቅ ሀገር ናት። በቅኝ አለመገዛቷ የኩራቷ እንጂ የድህነቷ መንስኤ አይደለም።
የኢትዮጵያ ዘመናዊ የኢኮኖሚ ፈተናዎች የመነጩት ከነጻነቷ ሳይሆን፣ በዙሪያዋ ከነበሩት የቅኝ ገዥ ኃይሎች ሴራ እና ከውስጣዊ ፖለቲካዊ ውጣ ውረዶች ነው። მላው አፍሪካ በቅኝ ግዛት ሲከፋፈል፣ ነጻዋ ኢትዮጵያ በቅኝ ገዥዎች ተከባ የባህር በር እንድታጣ እና ከዓለም አቀፍ ንግድ እንድትገለል ተደርጋለች። በቅርቡ ታሪክም በቀዝቃዛው ጦርነት የጂኦፖለቲካዊ ሽኩቻ ሰለባ በመሆን፣ እንዲሁም ደርግ በተከተለው አውዳሚ የማርክሲስት የኢኮኖሚ ሥርዓት እና በተራዘሙ የእርስ በርስ ጦርነቶች ምክንያት ኢኮኖሚዋ ክፉኛ ተጎድቷል። እነዚህ ሁሉ ፈተናዎች ቢኖሩም፣ ኢትዮጵያ የራሷን ቋንቋ፣ ባህል፣ የቀን አቆጣጠር እና ሀገራዊ ኩራት ጠብቃ ያቆየች፤ ዛሬም በአፍሪካ ቀንድ ትልቅ የኢኮኖሚ እና የፖለቲካ ተጽዕኖ ፈጣሪ መሆን የቻለች ሀገር ናት።
የአፍሪካን ወቅታዊ ችግሮች ለመፍታት ራስን መመርመር፣ ሙስናን መዋጋት እና የተሻለ አስተዳደር መገንባት አማራጭ የሌለው ጉዳይ ነው። ነገር ግን ይህንን ለማድረግ ሲባል የቅኝ ግዛትን አስከፊነት ማጠብ እና የኢትዮጵያን ደማቅ የነጻነት ታሪክ ማጠልሸት አይቻልም። ኢትዮጵያ ምንም እንኳን የኢኮኖሚ ፈተናዎች ቢኖሩባትም፣ የማንም ቅኝ ገዥ ሎሌ ሳትሆን የራሷን ዕድል በራሷ የወሰነች የአፍሪካ የቁርጥ ቀን ልጅ ናት። አህጉሪቱ ወደፊት መራመድ ያለባት የቅኝ ግዛትን ጠባሳ በማስተባበል ሳይሆን፣ እንደ ኢትዮጵያ ሁሉ የራስን ማንነት አጥብቆ በመያዝ እና ጠንካራ ኢኮኖሚን በነጻነት ላይ በመገንባት ሊሆን ይገባል።
11 days ago
መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በመላ ኢትዮጵያ ሊስፋፋ የሚገባው ተሞክሮ ነው
***************
አዲስ አበባ 8ኛውን አዲስ መሶብ የአንድ ማዕከል ዲጂታል አገልግሎት ማዕከል ወደ ሥራ
አስገብታለች።
ማዕከሉ በርካታ የመንግሥት አገልግሎቶችን በአንድ ጣሪያ ሥር በማሰባሰብ፣ ዜጎችን የሚያማርሩ የእጅ መንሻ እና አሰልቺ የቢሮክራሲ ሒደቶችን አስቀርቷል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን በማስፋፋት ረገድ ያከናወነው ሥራም ሌሎች የኢትዮጵያ ከተሞችና የክልል መስተዳድሮች ልምድ የሚሆን አርዓያነት ያለው ተግባር ነው።
በተለያዩ ክልሎችን ከተሞች መሰል የአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫዎች ቢቋቋሙም አሁንም ይበልጥ ሊሰራበት የሚገባ ጉዳይ መሆኑ አያጠያይቅም።
መሰል የዲጂታል ማዕከላት በየክልሉ መስፋፋታቸው፣ ወጥና ቀልጣፋ የአገልግሎት ሥርዓት እንዲዘረጋ በማድረግና ቅልጥፍናን በመጨመር የዜጎችን የእንግልት ለመቀነስ ያስችላል።
በመሆኑም የአዲስ መሶብን ተሞክሮ በመላ ኢትዮጵያ በማስፋት፣ ዜጎች ካለእንግልትና ከሙስና በጸዳ መልኩ ተገቢውን አገልግሎት የሚያገኙበትን ሥርዓት መዘርጋት ወቅቱ የሚጠይቀው ተግባር ነው።
#ebc #mesob #modern #service #addisababa
***************
አዲስ አበባ 8ኛውን አዲስ መሶብ የአንድ ማዕከል ዲጂታል አገልግሎት ማዕከል ወደ ሥራ
አስገብታለች።
ማዕከሉ በርካታ የመንግሥት አገልግሎቶችን በአንድ ጣሪያ ሥር በማሰባሰብ፣ ዜጎችን የሚያማርሩ የእጅ መንሻ እና አሰልቺ የቢሮክራሲ ሒደቶችን አስቀርቷል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን በማስፋፋት ረገድ ያከናወነው ሥራም ሌሎች የኢትዮጵያ ከተሞችና የክልል መስተዳድሮች ልምድ የሚሆን አርዓያነት ያለው ተግባር ነው።
በተለያዩ ክልሎችን ከተሞች መሰል የአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫዎች ቢቋቋሙም አሁንም ይበልጥ ሊሰራበት የሚገባ ጉዳይ መሆኑ አያጠያይቅም።
መሰል የዲጂታል ማዕከላት በየክልሉ መስፋፋታቸው፣ ወጥና ቀልጣፋ የአገልግሎት ሥርዓት እንዲዘረጋ በማድረግና ቅልጥፍናን በመጨመር የዜጎችን የእንግልት ለመቀነስ ያስችላል።
በመሆኑም የአዲስ መሶብን ተሞክሮ በመላ ኢትዮጵያ በማስፋት፣ ዜጎች ካለእንግልትና ከሙስና በጸዳ መልኩ ተገቢውን አገልግሎት የሚያገኙበትን ሥርዓት መዘርጋት ወቅቱ የሚጠይቀው ተግባር ነው።
#ebc #mesob #modern #service #addisababa
11 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) ዶናልድ ትራምፕ በሚኒሶታ ስለተፈጠረው ማጭበርበር የሐሰት ወሬ በማሰራጨት "እጅግ ብልሹ" ሲሉ እንደወነጀሏቸው የገለጹት የኮንግረስ አባል ኢልሃን ዑመር፣ ይህ ድርጊት የትራምፕ የራሳቸው ውድቀቶች እና ሙስናዎች ሲጋለጡባቸው በእሳቸው እና በሶማሌ ማኅበረሰብ ላይ ጥላቻን ለመቀስቀስ የሚጠቀሙበት የተለመደ ስልት መሆኑን አስታውቀዋል። አቅጣጫን የማስቀየር፣ የዘረኝነት እና የውሸት ፖለቲካ የትራምፕ ዋነኛ መገለጫ መሆኑንም አጽንኦት ሰጥተዋል።
ይህ የትራምፕ አካሄድ አዲስ ስልት እንዳልሆነ ያነሱት ኢልሃን ዑመር፣ የቀድሞው የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ሊንደን ቢ ጆንሰንን ጠቅሰዋል። ፕሬዚዳንቱ በወቅቱ እንዳሉት አንድን ዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ ያለ ነጭ ሰው ከምርጥ ጥቁር ሰው እንደሚበልጥ ማሳመን ከተቻለ፣ ኪሱ ሲዘረፍ እንኳ አያስተውልም፤ እንዲያውም የሚንቀው ሰው ከተሰጠው የራሱን ኪስ አራግፎ ይሰጣል ብለው ነበር። ኢልሃን ዑመር ይህንኑ ንግግር በማስታወስ፣ ትራምፕ ጥቁሮችን እና ነጮች ያልሆኑ ማኅበረሰቦችን በማንቋሸሽ ሕዝቡ እሱ ራሱ በጠራራ ፀሐይ የሀገር ሀብት ሲመዘብር እንዳያስተውል እያደረገ ይገኛል ብለዋል። ማጭበርበርን እንደ ፖለቲካዊ መሣሪያ እየተጠቀመ የራሱን የገንዘብ ደጋፊዎች እንደሚጠብቅ እና ራሱን እንደሚያበለጽግም ተችተዋል።
ትራምፕ ማጭበርበርን ስለመከላከል ምንም ደንታ እንደሌለው የገለጹት የምክር ቤት አባሏ፣ በተቃራኒው በጤና አጠባበቅ እና በባንክ ዘርፍ በሚሊዮኖች እና በቢሊዮኖች የሚቆጠር ዶላር ያጭበረበሩ እና የተፈረደባቸውን ግለሰቦች በይቅርታ እንደለቀቀ አጋልጠዋል። ከነዚህም መካከል በጤና ዘርፍ ታይቶ የማይታወቅ ማጭበርበር የፈጸሙ እና በመቶ ሚሊዮኖች የሚቆጠር ገንዘብ የዘረፉ ታላላቅ ወንጀለኞች ይገኙበታል። አሁን ደግሞ በጥር 6ቱ የካፒቶል ሁከት ፖሊሶችን ለደበደቡ እና ሕንጻውን ላወደሙ ግለሰቦች የካሳ ክፍያ የሚሆን እጅግ ግዙፍ ፈንድ ከሕዝብ ግብር በመመደብ አሜሪካውያንን በድጋሚ እያጭበረበረ መሆኑን አብራርተዋል።
ማጭበርበር የትም ይከሰት የት መወገድ እንዳለበት ያመላከቱት ኢልሃን ዑመር፣ ሕፃናትን ለመመገብ የተመደበን በጀት ያጭበረበሩ ግለሰቦች ያለ ምንም ልዩነት በሕግ ሊጠየቁ ይገባል ብለዋል። በልጅነታቸው በስደተኞች መጠለያ ካምፕ ውስጥ የረሃብን ስቃይ እንዳሳለፉ በማስታወስ፣ የራሳቸውን ልጆች የሚመግቡት አጥተው ሲራቡ ማየት ለወላጆች ምን ያህል አሳዛኝ እንደሆነ በሚገባ እንደሚረዱ ገልጸዋል። በመሆኑም ሕፃናትን ከረሃብ ለመታደግ የተቋቋመን ፕሮግራም በግል ጥቅም መበዝበዝ እጅግ አሳፋሪ እና ጸያፍ ተግባር መሆኑን በመጥቀስ፣ ወንጀሉ ሲጋለጥ ጀምሮ ፈጻሚዎቹ ለሕግ እንዲቀርቡ ጠንካራ ጥያቄ ሲያቀርቡ መቆየታቸውን አስታውሰዋል።
ሚኒሶታ ውስጥ የተፈጸመውን ይህንን ወንጀል የፖለቲካ ትርፍ ማግኛ ካደረጉት ትራምፕ እና ሪፐብሊካኖች በተቃራኒ፣ የሚኒሶታ አመራሮች አጭበርባሪዎቹን ለሕግ በማቅረብ ረጅም የእስር ቅጣት እንዲተላለፍባቸው ማድረጋቸውን ጠቁመዋል። ትራምፕ ሌቦችን ከእስር ሲለቅ፣ የክልሉ አመራሮች ግን እውነተኛ ተጠያቂነትን በተግባር በማሳየት ወንጀለኞችን ከርቸሌ አውርደዋል ብለዋል።
የትራምፕ ቤተሰብ ከዘመናዊ የዲጂታል ገንዘብ ግብይት ትርፍ እያጋበሰ እና የፕሬዚዳንትነት ሥልጣን ለሽያጭ የቀረበ እስኪመስል ድረስ የግል ብልጽግናን እያሳደደ መሆኑን የጠቀሱት ዑመር፣ የትራምፕ ዩኒቨርሲቲን ማጭበርበር እና የበጎ አድራጎት ተቋሙን ሕገ-ወጥ አሠራር በምሳሌነት አንስተዋል። በመጨረሻም፣ ትራምፕ የራሱን ሙስና ለመሸፈን ዘረኛ የሆኑ የፈጠራ ወሬዎችን እንደሚያሰራጭ በመግለጽ፣ በአሜሪካ ታሪክ ውስጥ እንዳሱ ያለ ታላቅ አጭበርባሪ ታይቶ አያውቅም ሲሉ ጽሑፋቸውን ቋጭተዋል።
ይህ የትራምፕ አካሄድ አዲስ ስልት እንዳልሆነ ያነሱት ኢልሃን ዑመር፣ የቀድሞው የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ሊንደን ቢ ጆንሰንን ጠቅሰዋል። ፕሬዚዳንቱ በወቅቱ እንዳሉት አንድን ዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ ያለ ነጭ ሰው ከምርጥ ጥቁር ሰው እንደሚበልጥ ማሳመን ከተቻለ፣ ኪሱ ሲዘረፍ እንኳ አያስተውልም፤ እንዲያውም የሚንቀው ሰው ከተሰጠው የራሱን ኪስ አራግፎ ይሰጣል ብለው ነበር። ኢልሃን ዑመር ይህንኑ ንግግር በማስታወስ፣ ትራምፕ ጥቁሮችን እና ነጮች ያልሆኑ ማኅበረሰቦችን በማንቋሸሽ ሕዝቡ እሱ ራሱ በጠራራ ፀሐይ የሀገር ሀብት ሲመዘብር እንዳያስተውል እያደረገ ይገኛል ብለዋል። ማጭበርበርን እንደ ፖለቲካዊ መሣሪያ እየተጠቀመ የራሱን የገንዘብ ደጋፊዎች እንደሚጠብቅ እና ራሱን እንደሚያበለጽግም ተችተዋል።
ትራምፕ ማጭበርበርን ስለመከላከል ምንም ደንታ እንደሌለው የገለጹት የምክር ቤት አባሏ፣ በተቃራኒው በጤና አጠባበቅ እና በባንክ ዘርፍ በሚሊዮኖች እና በቢሊዮኖች የሚቆጠር ዶላር ያጭበረበሩ እና የተፈረደባቸውን ግለሰቦች በይቅርታ እንደለቀቀ አጋልጠዋል። ከነዚህም መካከል በጤና ዘርፍ ታይቶ የማይታወቅ ማጭበርበር የፈጸሙ እና በመቶ ሚሊዮኖች የሚቆጠር ገንዘብ የዘረፉ ታላላቅ ወንጀለኞች ይገኙበታል። አሁን ደግሞ በጥር 6ቱ የካፒቶል ሁከት ፖሊሶችን ለደበደቡ እና ሕንጻውን ላወደሙ ግለሰቦች የካሳ ክፍያ የሚሆን እጅግ ግዙፍ ፈንድ ከሕዝብ ግብር በመመደብ አሜሪካውያንን በድጋሚ እያጭበረበረ መሆኑን አብራርተዋል።
ማጭበርበር የትም ይከሰት የት መወገድ እንዳለበት ያመላከቱት ኢልሃን ዑመር፣ ሕፃናትን ለመመገብ የተመደበን በጀት ያጭበረበሩ ግለሰቦች ያለ ምንም ልዩነት በሕግ ሊጠየቁ ይገባል ብለዋል። በልጅነታቸው በስደተኞች መጠለያ ካምፕ ውስጥ የረሃብን ስቃይ እንዳሳለፉ በማስታወስ፣ የራሳቸውን ልጆች የሚመግቡት አጥተው ሲራቡ ማየት ለወላጆች ምን ያህል አሳዛኝ እንደሆነ በሚገባ እንደሚረዱ ገልጸዋል። በመሆኑም ሕፃናትን ከረሃብ ለመታደግ የተቋቋመን ፕሮግራም በግል ጥቅም መበዝበዝ እጅግ አሳፋሪ እና ጸያፍ ተግባር መሆኑን በመጥቀስ፣ ወንጀሉ ሲጋለጥ ጀምሮ ፈጻሚዎቹ ለሕግ እንዲቀርቡ ጠንካራ ጥያቄ ሲያቀርቡ መቆየታቸውን አስታውሰዋል።
ሚኒሶታ ውስጥ የተፈጸመውን ይህንን ወንጀል የፖለቲካ ትርፍ ማግኛ ካደረጉት ትራምፕ እና ሪፐብሊካኖች በተቃራኒ፣ የሚኒሶታ አመራሮች አጭበርባሪዎቹን ለሕግ በማቅረብ ረጅም የእስር ቅጣት እንዲተላለፍባቸው ማድረጋቸውን ጠቁመዋል። ትራምፕ ሌቦችን ከእስር ሲለቅ፣ የክልሉ አመራሮች ግን እውነተኛ ተጠያቂነትን በተግባር በማሳየት ወንጀለኞችን ከርቸሌ አውርደዋል ብለዋል።
የትራምፕ ቤተሰብ ከዘመናዊ የዲጂታል ገንዘብ ግብይት ትርፍ እያጋበሰ እና የፕሬዚዳንትነት ሥልጣን ለሽያጭ የቀረበ እስኪመስል ድረስ የግል ብልጽግናን እያሳደደ መሆኑን የጠቀሱት ዑመር፣ የትራምፕ ዩኒቨርሲቲን ማጭበርበር እና የበጎ አድራጎት ተቋሙን ሕገ-ወጥ አሠራር በምሳሌነት አንስተዋል። በመጨረሻም፣ ትራምፕ የራሱን ሙስና ለመሸፈን ዘረኛ የሆኑ የፈጠራ ወሬዎችን እንደሚያሰራጭ በመግለጽ፣ በአሜሪካ ታሪክ ውስጥ እንዳሱ ያለ ታላቅ አጭበርባሪ ታይቶ አያውቅም ሲሉ ጽሑፋቸውን ቋጭተዋል።
13 days ago
በትራምፕ እና በኔታንያሁ መካከል የተካሄደው የቁጣ ስልክ ጥሪ
“ምንድነው የምታደርገው?” ትራምፕ
ኢራን በእስራኤል የሊባኖስ ዘመቻ ምክንያት ከአሜሪካ ጋር የምታደርገውን ንግግር እንደምታቋርጥ ከተናገረች በኋላ፣ በሁለቱ መሪዎች መካከል የቁጣ የስልክ ጥሪ ልውውጥ መደረጉ ተነገረ
ዶናልድ ትራምፕ ቤሩት ደቡባዊ የከተማ ዳርቻዎች ላይ የአየር ጥቃት ለመጀመር በመዛቱ ምክንያት የእስራኤሉን ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንጃሚን ኔታንያሁን በቁጣ መጋፈጣቸውን አንድ ዘገባ አመልክቷል።
በሁለቱ መሪዎች መካከል የሚደረጉ ከፍተኛ የደረጃ ውይይቶችን በተደጋጋሚ ይፋ የሚያደርገው ‘አክሲዮስ’ የተሰኘው የአሜሪካ ድረ-ገጽ እንደዘገበው፤ ሰኞ ዕለት በተደረገው የስልክ ጥሪ ላይ የአሜሪካው ፕሬዚዳንት በእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ላይ “ምንድነው የምታደርገው?” በማለት በቁጣ ጮኸውባቸዋል።
በእስራኤል መገናኛ ብዙሃን መካድ የገጠመው ይህ ዘገባ፣ አንድ የአሜሪካ ባለስልጣን ትራምፕ ለኔታንያሁ የተናገሩትን ሲያጠቃልሉ፦ **“አብደሃል። እኔ ባልኖር ኖሮ አሁን እስር ቤት ነበርክ። እኔ ነኝ እያዳንኩህ ያለሁት። አሁን ሁሉም ሰው ይጠላሃል። በዚህ ምክንያት ሁሉም ሰው እስራኤልን እየጠላት ነው”ማለታቸውን ጠቅሷል።
የስልክ ጥሪው የተደረገው ኔታንያሁ የእስራኤል ጦር ወደ እስራኤል የድሮን ጥቃቶችን ለሰነዘረውና በኢራን ለሚደገፈው የሂዝቦላ ሚሊሺያ ኢላማ ለማድረግ በቤሩት ደቡባዊ ዳሂያ አካባቢ ላይ የቦምብ ጥቃት እንዲጀምር ትዕዛዝ ከሰጡ በኋላ ነው።
የእስራኤል መከላከያ ሰራዊት በደቡብ ቤሩት የሚኖሩ የሊባኖስ ሲቪሎች አካባቢውን ለቀው እንዲወጡ ማሳሰቢያ የሰጠ ሲሆን፣ ይህንን ተከትሎም በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ተሰደዋል።
ኢራን ማክሰኞ ዕለት በሰጠችው መግለጫ፤ እስራኤል በደቡብ ሊባኖስ እያካሄደች ባለው ዘመቻ ምክንያት ከአሜሪካ ጋር የምታደርገውን የሰላም ንግግር እንደምታቋርጥ አስታውቃለች።
ቴህራን የሆርሙዝ የባህር ወሽመጥን ለመክፈትና አሜሪካ በኢራን ወደቦች ላይ የጣለችውን እገዳ ለማንሳት የሚደረጉ ድርድሮችን ለማመቻቸት ሲባል፣ ሊባኖስም የተኩስ አቁም ስምምነቱ አካል መሆን አለባት ስትል ሞግታለች።
በኮንትሮባንድና የንግግር ማቋረጥ ዙሪያ የተሰማው ይህ መግለጫ፤ ትራምፕ ተደራዳሪዎች ሊፈርሙበት የሚችሉትን የመጀመሪያ ደረጃ ስምምነት ላይ መድረሳቸውንና እሳቸውም ለመፈረም እያሰቡበት መሆኑን ከተናገሩ ከጥቂት ቀናት በኋላ የተሰማ ሲሆን፣ በሁለቱ መሪዎች መካከል የተደረገው የስልክ ጥሪም ይህንን ተከትሎ የመጣ ነው።
ቻናል 12 (Channel 12) የተሰኘው ታዋቂና ገለልተኛ የእስራኤል የዜና አውታር ግን የጥሪውን ዝርዝር መረጃ አስተባብሏል። የጣቢያው ዋና የፖለቲካ ተንታኝ አሚት ሴጋል እንዳለው፤ ትራምፕ በኔታንያሁ ላይ ግላዊ ጥቃት እንዳልሰነዘሩና ሁለቱ መሪዎች ሂዝቦላ በእስራኤል ላይ የሚያደርገውን ጥቃት ካቆመ፣ እስራኤልም በቤሩት የከተማ ዳርቻዎች ላይ ጥቃት ከመሰንዘር እንድትቆጠብ ስምምነት ላይ መድረሳቸውን ገልጿል።
በኔታንያሁ እና በትራምፕ ጥምረት መካከል የተፈጠረው ውጥረት
ምንም እንኳን እስራኤል በአካባቢው የአሜሪካ ዋና አጋር ሆና ብትቀጥልም እና ሁለቱ መሪዎች በየካቲት ወር በኔታንያሁ ግፊት በኢራን ላይ በጋራ ጥቃት ቢሰነዝሩም፣ ትራምፕና ኔታንያሁ ባለፈው ጊዜ የሻከረ ግንኙነት ነበራቸው።
ትራምፕ ባለፈው ዓመት የአየር ኃይል፣ ሚሳኤሎችና ድሮኖችን ያካተተ የ12 ቀናት የጋራ ጥቃት ልውውጥ በተደረገበት ወቅት ኢራን እና እስራኤል ምን እያደረጉ እንደሆነ አያውቁም በማለት በይፋ ተቆጥተው ነበር።
ኔታንያሁ ጆ ባይደንን በ2020 ትራምፕ በተቃወሙት ምርጫ ማሸነፋቸውን ተከትሎ የእንኳን አደረሰህ መልዕክት ካስተላለፉ በኋላ፣ ትራምፕ ስለ ኔታንያሁ ሲናገሩ ጠንከር ያለ የስድብ ቃል ተጠቅመው ነበር።
ትራምፕ ከተለያዩ የሪፐብሊካን ፓርቲ ክፍሎች ጫና እየገጠማቸው ነው። ለአይሁድ ደጋፊ የሆኑ አጋሮቻቸው አሜሪካ ከኢራን ጋር ባላት ግጭት የበለጠ እንድትገፋበት ሲጠይቁ፣ ሌሎች ደግሞ ከኖቬምበር የዩኤስ የአጋማሽ ዘመን ምርጫ በፊት የሚደርሰውን ኢኮኖሚያዊ ጉዳት ለመቀነስ ጦርነቱ በአስቸኳይ እንዲያበቃ ይፈልጋሉ።
ከትራምፕ ጋር የሚነጋገረውና ተጽዕኖ ፈጣሪ የሆነው ፕሮ-እስራኤል የቶክ ሾው አቅራቢ ማርክ ሌቪን እንደጻፈው፤ “የኢራን አገዛዝ ከዚህ መረጃ መውጣት (Leak) ተጠቃሚ ይሆናል፣ እኛን ደካማና ለስምምነት የምንቸኩል አድርጎ ይመለከተናል - አልፎ ተርፎም ለሂዝቦላ ጥበቃ እንደመቆም ይቆጥረዋል” ብሏል።
ኔታንያሁም ቢሆኑ በፖለቲካዊ ጫና ውስጥ ናቸው።
የእስራኤል ፓርላማ በዚህ ሳምንት ክኔሴትን (Knesset) ለመበተን እና ቅድመ ምርጫ ለመጥራት የቀረበውን ረቂቅ አዋጅ በመጀመሪያ ንባብ የደገፈው ሲሆን፣ በእስራኤል የደህንነት ሁኔታ ምክንያት በተደጋጋሚ ተራዝሞ የነበረው የሙስና ክስ ችሎታቸውም እንዲቀጥል ቀጠሮ ተይዟል።
“ምንድነው የምታደርገው?” ትራምፕ
ኢራን በእስራኤል የሊባኖስ ዘመቻ ምክንያት ከአሜሪካ ጋር የምታደርገውን ንግግር እንደምታቋርጥ ከተናገረች በኋላ፣ በሁለቱ መሪዎች መካከል የቁጣ የስልክ ጥሪ ልውውጥ መደረጉ ተነገረ
ዶናልድ ትራምፕ ቤሩት ደቡባዊ የከተማ ዳርቻዎች ላይ የአየር ጥቃት ለመጀመር በመዛቱ ምክንያት የእስራኤሉን ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንጃሚን ኔታንያሁን በቁጣ መጋፈጣቸውን አንድ ዘገባ አመልክቷል።
በሁለቱ መሪዎች መካከል የሚደረጉ ከፍተኛ የደረጃ ውይይቶችን በተደጋጋሚ ይፋ የሚያደርገው ‘አክሲዮስ’ የተሰኘው የአሜሪካ ድረ-ገጽ እንደዘገበው፤ ሰኞ ዕለት በተደረገው የስልክ ጥሪ ላይ የአሜሪካው ፕሬዚዳንት በእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ላይ “ምንድነው የምታደርገው?” በማለት በቁጣ ጮኸውባቸዋል።
በእስራኤል መገናኛ ብዙሃን መካድ የገጠመው ይህ ዘገባ፣ አንድ የአሜሪካ ባለስልጣን ትራምፕ ለኔታንያሁ የተናገሩትን ሲያጠቃልሉ፦ **“አብደሃል። እኔ ባልኖር ኖሮ አሁን እስር ቤት ነበርክ። እኔ ነኝ እያዳንኩህ ያለሁት። አሁን ሁሉም ሰው ይጠላሃል። በዚህ ምክንያት ሁሉም ሰው እስራኤልን እየጠላት ነው”ማለታቸውን ጠቅሷል።
የስልክ ጥሪው የተደረገው ኔታንያሁ የእስራኤል ጦር ወደ እስራኤል የድሮን ጥቃቶችን ለሰነዘረውና በኢራን ለሚደገፈው የሂዝቦላ ሚሊሺያ ኢላማ ለማድረግ በቤሩት ደቡባዊ ዳሂያ አካባቢ ላይ የቦምብ ጥቃት እንዲጀምር ትዕዛዝ ከሰጡ በኋላ ነው።
የእስራኤል መከላከያ ሰራዊት በደቡብ ቤሩት የሚኖሩ የሊባኖስ ሲቪሎች አካባቢውን ለቀው እንዲወጡ ማሳሰቢያ የሰጠ ሲሆን፣ ይህንን ተከትሎም በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ተሰደዋል።
ኢራን ማክሰኞ ዕለት በሰጠችው መግለጫ፤ እስራኤል በደቡብ ሊባኖስ እያካሄደች ባለው ዘመቻ ምክንያት ከአሜሪካ ጋር የምታደርገውን የሰላም ንግግር እንደምታቋርጥ አስታውቃለች።
ቴህራን የሆርሙዝ የባህር ወሽመጥን ለመክፈትና አሜሪካ በኢራን ወደቦች ላይ የጣለችውን እገዳ ለማንሳት የሚደረጉ ድርድሮችን ለማመቻቸት ሲባል፣ ሊባኖስም የተኩስ አቁም ስምምነቱ አካል መሆን አለባት ስትል ሞግታለች።
በኮንትሮባንድና የንግግር ማቋረጥ ዙሪያ የተሰማው ይህ መግለጫ፤ ትራምፕ ተደራዳሪዎች ሊፈርሙበት የሚችሉትን የመጀመሪያ ደረጃ ስምምነት ላይ መድረሳቸውንና እሳቸውም ለመፈረም እያሰቡበት መሆኑን ከተናገሩ ከጥቂት ቀናት በኋላ የተሰማ ሲሆን፣ በሁለቱ መሪዎች መካከል የተደረገው የስልክ ጥሪም ይህንን ተከትሎ የመጣ ነው።
ቻናል 12 (Channel 12) የተሰኘው ታዋቂና ገለልተኛ የእስራኤል የዜና አውታር ግን የጥሪውን ዝርዝር መረጃ አስተባብሏል። የጣቢያው ዋና የፖለቲካ ተንታኝ አሚት ሴጋል እንዳለው፤ ትራምፕ በኔታንያሁ ላይ ግላዊ ጥቃት እንዳልሰነዘሩና ሁለቱ መሪዎች ሂዝቦላ በእስራኤል ላይ የሚያደርገውን ጥቃት ካቆመ፣ እስራኤልም በቤሩት የከተማ ዳርቻዎች ላይ ጥቃት ከመሰንዘር እንድትቆጠብ ስምምነት ላይ መድረሳቸውን ገልጿል።
በኔታንያሁ እና በትራምፕ ጥምረት መካከል የተፈጠረው ውጥረት
ምንም እንኳን እስራኤል በአካባቢው የአሜሪካ ዋና አጋር ሆና ብትቀጥልም እና ሁለቱ መሪዎች በየካቲት ወር በኔታንያሁ ግፊት በኢራን ላይ በጋራ ጥቃት ቢሰነዝሩም፣ ትራምፕና ኔታንያሁ ባለፈው ጊዜ የሻከረ ግንኙነት ነበራቸው።
ትራምፕ ባለፈው ዓመት የአየር ኃይል፣ ሚሳኤሎችና ድሮኖችን ያካተተ የ12 ቀናት የጋራ ጥቃት ልውውጥ በተደረገበት ወቅት ኢራን እና እስራኤል ምን እያደረጉ እንደሆነ አያውቁም በማለት በይፋ ተቆጥተው ነበር።
ኔታንያሁ ጆ ባይደንን በ2020 ትራምፕ በተቃወሙት ምርጫ ማሸነፋቸውን ተከትሎ የእንኳን አደረሰህ መልዕክት ካስተላለፉ በኋላ፣ ትራምፕ ስለ ኔታንያሁ ሲናገሩ ጠንከር ያለ የስድብ ቃል ተጠቅመው ነበር።
ትራምፕ ከተለያዩ የሪፐብሊካን ፓርቲ ክፍሎች ጫና እየገጠማቸው ነው። ለአይሁድ ደጋፊ የሆኑ አጋሮቻቸው አሜሪካ ከኢራን ጋር ባላት ግጭት የበለጠ እንድትገፋበት ሲጠይቁ፣ ሌሎች ደግሞ ከኖቬምበር የዩኤስ የአጋማሽ ዘመን ምርጫ በፊት የሚደርሰውን ኢኮኖሚያዊ ጉዳት ለመቀነስ ጦርነቱ በአስቸኳይ እንዲያበቃ ይፈልጋሉ።
ከትራምፕ ጋር የሚነጋገረውና ተጽዕኖ ፈጣሪ የሆነው ፕሮ-እስራኤል የቶክ ሾው አቅራቢ ማርክ ሌቪን እንደጻፈው፤ “የኢራን አገዛዝ ከዚህ መረጃ መውጣት (Leak) ተጠቃሚ ይሆናል፣ እኛን ደካማና ለስምምነት የምንቸኩል አድርጎ ይመለከተናል - አልፎ ተርፎም ለሂዝቦላ ጥበቃ እንደመቆም ይቆጥረዋል” ብሏል።
ኔታንያሁም ቢሆኑ በፖለቲካዊ ጫና ውስጥ ናቸው።
የእስራኤል ፓርላማ በዚህ ሳምንት ክኔሴትን (Knesset) ለመበተን እና ቅድመ ምርጫ ለመጥራት የቀረበውን ረቂቅ አዋጅ በመጀመሪያ ንባብ የደገፈው ሲሆን፣ በእስራኤል የደህንነት ሁኔታ ምክንያት በተደጋጋሚ ተራዝሞ የነበረው የሙስና ክስ ችሎታቸውም እንዲቀጥል ቀጠሮ ተይዟል።
Sponsored by
Surafel
20 days ago
(ዘ-ሐበሻ ነቆራ) በቋንቋችን ውስጥ መዝገበ-ቃላት እና እውነታ ሁሌም የድመትና አይጥ ጸብ አላቸው። ለምሳሌ "ጉቦ" የሚለውን ቃል ብትወስድ፣ ቃሉ ራሱ ሲጠራ ልክ እንደ ደረቅ ሳል ጆሮ ይጎረብጣል። ስለዚህ ዘመናዊዎቹ የኪስ ጠላፊዎች፣ ለጆሮ እንዲጥም "የማበረታቻ ሽልማት"፣ "የእጅ መንሻ" ወይም "የፍቅር ስጦታ" እያሉ አቆላምጠውታል። ሙስና በሀገራችን ስሟን እንደቀየረች ኮከብ ዘፋኝ አዲስ ገጽታ ተላብሳለች።
ሰሞኑን ታዲያ አንዱ ስማቸውን ለጊዜው የማልጠቅስላችሁ ባለሀብት አንድ ባለስልጣን ቢሮ ብቅ ይላሉ። አረማመዳቸው ራሱ "ጨረታ ስጠኝ" የሚል ዜማ አለው። እጃቸውን ደረታቸው ላይ አጣምረው፣ አንገታቸውን እንደ ጤፍ ዛላ ሰብረው፣ የጂ-ፕላስ-ስሪ ቪላ ቁልፍ ከነሙሉ እቃው፣ ለክቡር ሚኒስትሩ አቀረቡ።
ሚኒስትሩ የህዝብ ብሶት ከረባት አድርጎ ያነቃቸው ይመስል፣ ፊታቸውን እንደ ጦርነት ዋዜማ አኮሳትረው.. “ይሄ ምንድነው አንተ ሰው?” ብለው በቁጣ ጠየቁ።
ባለሃብቱም የቃላት ዶክተር ናቸውና፣ ድምፃቸውን እንደ ማታ ራዲዮ አሳምረው እንዲህ አሉ.. “ክቡር ሚኒስትር... የህዝቡ አደራ ጫንቃዎ ላይ ሲወጣ ሲወርድ አከርካሪዎን እንዳይጎዳው፣ እንዲሁም የሀገሪቱ ጉዳይ ሀሳብ ሲያበዛብዎት፣ ከከተማው ትርምስ ራቅ ብለው ንጹህ አየር የሚቀበሉባት... አንዲት ጠባብ ባለ ሶስት ፎቅ የሳር ጎጆ አዘጋጅቼልዎት ነው።”
ባለስልጣኑ የቁልፉን ብረት በስሱ እያሻሹ፣ ግን ደግሞ ቅሬታ እንደገባው ሰው አሁንም ፊታቸው አልተፈታም፡-
“አይ እናንተ ባለሃብቶች... ህዝብ እኮ አይን አለው! ፀረ-ሙስና የሚባል የጨጓራ በሽታስ ዝም ይላል? ደግሞ ጂ ፕላስ ስሪ መቼ ወዲህ ነው ጎጆ የሆነው? ይሄ እኮ ከባድ ሙስና ነው!”
ባለሃብቱ ግን መቼ ይደናገጣሉ? ቃላትን በወንፊት እያነጠሩ መለሱ፡-
“ለእርስዎ ትልቅነትማ ባለ ሶስት ፎቅ ቪላም ጎጆ እንጂ ምንድነው ጌታዬ! ደግሞም እኮ ይሄን የገዛሁት ለእርስዎ ብዬ አይደለም። እርስዎ ሲደክምዎት ውሳኔ እንዳይዛባብዎት፣ እረፍት አግኝተው ለህዝቡ የተሻለ ስራ እንዲሰሩ በማሰብ... ለህዝቡ ስል የገዛሁት 'የህዝብ ቤት' ነው። እርሶ በህዝብ ስም ይረፉበት ብዬ ነው።”
ይሄን ጊዜ በሚኒስትሩ ፊት ላይ የነበረው ደመና በአንድ ጊዜ ተገፎ በፀደይ ፀሀይ ተተካ። ቁልፉን ወደ ኪሳቸው እያሸረተቱ፣ “እህህ... አየህ አንተ ሰው፣ ለህዝቡ ጥቅም ከሆነማ... እኔ ማነኝና የህዝብን ስጦታ እመልሳለሁ? የህዝብን አደራ አለመቀበል እኮ ትዕቢት ነው!” ብለው የህዝቡን ቪላ፣ በህዝቡ ስም፣ በራሳቸው ካርታ አዙረውታል። በሀገራችን "ሌብነት" እና "ብልህነት" አንድ አባትና እናት እንዳላቸው መንታ ልጆች ናቸው፤ የሚለዩት በለበሱት የሹመት ካፖርት ብቻ ነው!
በማግስቱ ታዲያ ነገሮች እንደ ጃፓን ባቡር ፈጠኑ። የሚኒስትሩ መሥሪያ ቤት ያወጣው የብዙ መቶ ሚሊዮን ብር ግዙፍ ፕሮጀክት የጨረታ ውጤት ሲለጠፍ፣ አሸናፊው ሩቅ አልነበረም። ያው "የህዝቡን ቪላ" አበርካች፣ የዘመናችን ሩህሩህ ቱጃር ሆነው እርፍ አሉ!
ይሄን ጊዜ ሌሎቹ ተጫራቾች… ማለትም ጨረታ በወረቀት፣ በማህተምና በፊርማ ብቻ የሚሸነፍ የሚመስላቸው የዋሃን ነጋዴዎች… አንጀታቸው አረረ። “እንዴት እርሳቸው ያሸንፋሉ? የእኛ ዋጋ እኮ በጣም አነስተኛ ነበር! የቴክኒክ ሰነዳችንም ቢሆን ከአውሮፓ ስታንዳርድ የሚስተካከል ነበር!” በማለት የጨረታ ኮሚቴውን አፍጠው ጠየቁ።
ኮሚቴው መልስ ቢያጣ፣ ጉዳዩ ወደ ክቡር ሚኒስትሩ ጆሮ ደረሰ። ሚኒስትሩ ግን ይህን ሲሰሙ ከመቆጣት ይልቅ፣ እንደ አንድ ሩቅ አላሚ "ልማታዊ አባት" ፈገግ አሉ። የተወሰኑትን ተጫራቾች ቢሯቸው አስጠርተው በለዘበ አንደበት እንዲህ ሲሉ የጨረታውን ስነ-መለኮት አስረዷቸው፡-
“እህህ... እናንተ ሰዎች ግብዞች ናችሁ፣ ፊደል እንጂ አገር አላነበባችሁም! የጨረታ ሰነድ ማለት እኮ በወረቀት ላይ የተጻፈ የውሸት ተስፋ ነው። እናንተ 'ነገ እንገነባለን፣ አቅሙ አለን፣ እናደርጋለን' ብላችሁ በባዶ ወረቀት ስታነበንቡ፣ አቶ [እገሌ] ግን ማታ አስቦ፣ ጧት ጂ-ፕላስ-ስሪ ቪላ አሰርቶ፣ ከነሙሉ ዕቃው ቁልፍ የሚያስረክብ 'የተግባር ሰው' መሆኑን ለህዝብ (ማለትም ለእኔ) በተጨባጭ አሳይቷል። ታዲያ ሀገር የምትለወጠው በወረቀት ቃል ኪዳን ነው ወይስ በተጨባጭ አቅርቦት?”
ተጫራቾቹ አንገታቸውን ደፉ። እውነትም መመዘኛውን አልተረዱትም ነበር። አቶ [እገሌ] የተባሉት ባለሃብት ጨረታውን ያሸነፉት "በቴክኒክ እና በፋይናንስ" ብቃት ሳይሆን፣ "በቅድመ-ክፍያ እና በፍቅር" ብቃት እንደሆነ አሁን ገባቸው። ደግሞም እኮ የአቶ እገሌ ሰነድ ከሌሎቹ የሚለየው በኮምፒውተር ታይፕ የተመታ ሳይሆን፣ በብሎኬት እና በኮንክሪት የታነጸ መሆኑ ነው።
ሚኒስትሩ ንግግራቸውን ሲያጠቃልሉ፣ “አቶ እገሌ ለዚህ መሥሪያ ቤት ያሳዩት 'የማስረከብ ፍጥነት' ወደር የሌለው ነው። ትናንት ማታ ቃል የገቡትን ቪላ... ይቅርታ ፕሮጀክት፣ ወዲያው ነው እጄ ላይ ያስቀመጡት። ስለዚህ የህዝቡን ፕሮጀክት ከእርሳቸው የተሻለ ማንም አያሳካውም!” በማለት በጭብጨባ አሰናበቷቸው።
በእርግጥም በሀገራችን የጨረታ ሳጥን የሚከፈተው በሰም እና በታሸገ ኤንቨሎፕ አይደለም፤ የጨረታ ሳጥን የሚከፈተው በቪላ በር ቁልፍ ነው! "የሰጠህን አብላው፣ የቀበጠህን አባርረው" የሚለው የቀድሞ አባቶቻችን ጥልቅ ፍልስፍና በዘመናዊው ቢሮክራሲ ውስጥ ሲተረጎም እንዲህ ያምራል። ባለሃብቱ ቤቱን ለህዝብ ሰጡ፣ ሚኒስትሩ ደግሞ የህዝቡን ፕሮጀክት ለባለሃብቱ ሰጡ። ፍትሃዊ የሀብት ክፍፍል ማለት ይሄው አይደል?
አበጀ በለው የላኩልን
ሰሞኑን ታዲያ አንዱ ስማቸውን ለጊዜው የማልጠቅስላችሁ ባለሀብት አንድ ባለስልጣን ቢሮ ብቅ ይላሉ። አረማመዳቸው ራሱ "ጨረታ ስጠኝ" የሚል ዜማ አለው። እጃቸውን ደረታቸው ላይ አጣምረው፣ አንገታቸውን እንደ ጤፍ ዛላ ሰብረው፣ የጂ-ፕላስ-ስሪ ቪላ ቁልፍ ከነሙሉ እቃው፣ ለክቡር ሚኒስትሩ አቀረቡ።
ሚኒስትሩ የህዝብ ብሶት ከረባት አድርጎ ያነቃቸው ይመስል፣ ፊታቸውን እንደ ጦርነት ዋዜማ አኮሳትረው.. “ይሄ ምንድነው አንተ ሰው?” ብለው በቁጣ ጠየቁ።
ባለሃብቱም የቃላት ዶክተር ናቸውና፣ ድምፃቸውን እንደ ማታ ራዲዮ አሳምረው እንዲህ አሉ.. “ክቡር ሚኒስትር... የህዝቡ አደራ ጫንቃዎ ላይ ሲወጣ ሲወርድ አከርካሪዎን እንዳይጎዳው፣ እንዲሁም የሀገሪቱ ጉዳይ ሀሳብ ሲያበዛብዎት፣ ከከተማው ትርምስ ራቅ ብለው ንጹህ አየር የሚቀበሉባት... አንዲት ጠባብ ባለ ሶስት ፎቅ የሳር ጎጆ አዘጋጅቼልዎት ነው።”
ባለስልጣኑ የቁልፉን ብረት በስሱ እያሻሹ፣ ግን ደግሞ ቅሬታ እንደገባው ሰው አሁንም ፊታቸው አልተፈታም፡-
“አይ እናንተ ባለሃብቶች... ህዝብ እኮ አይን አለው! ፀረ-ሙስና የሚባል የጨጓራ በሽታስ ዝም ይላል? ደግሞ ጂ ፕላስ ስሪ መቼ ወዲህ ነው ጎጆ የሆነው? ይሄ እኮ ከባድ ሙስና ነው!”
ባለሃብቱ ግን መቼ ይደናገጣሉ? ቃላትን በወንፊት እያነጠሩ መለሱ፡-
“ለእርስዎ ትልቅነትማ ባለ ሶስት ፎቅ ቪላም ጎጆ እንጂ ምንድነው ጌታዬ! ደግሞም እኮ ይሄን የገዛሁት ለእርስዎ ብዬ አይደለም። እርስዎ ሲደክምዎት ውሳኔ እንዳይዛባብዎት፣ እረፍት አግኝተው ለህዝቡ የተሻለ ስራ እንዲሰሩ በማሰብ... ለህዝቡ ስል የገዛሁት 'የህዝብ ቤት' ነው። እርሶ በህዝብ ስም ይረፉበት ብዬ ነው።”
ይሄን ጊዜ በሚኒስትሩ ፊት ላይ የነበረው ደመና በአንድ ጊዜ ተገፎ በፀደይ ፀሀይ ተተካ። ቁልፉን ወደ ኪሳቸው እያሸረተቱ፣ “እህህ... አየህ አንተ ሰው፣ ለህዝቡ ጥቅም ከሆነማ... እኔ ማነኝና የህዝብን ስጦታ እመልሳለሁ? የህዝብን አደራ አለመቀበል እኮ ትዕቢት ነው!” ብለው የህዝቡን ቪላ፣ በህዝቡ ስም፣ በራሳቸው ካርታ አዙረውታል። በሀገራችን "ሌብነት" እና "ብልህነት" አንድ አባትና እናት እንዳላቸው መንታ ልጆች ናቸው፤ የሚለዩት በለበሱት የሹመት ካፖርት ብቻ ነው!
በማግስቱ ታዲያ ነገሮች እንደ ጃፓን ባቡር ፈጠኑ። የሚኒስትሩ መሥሪያ ቤት ያወጣው የብዙ መቶ ሚሊዮን ብር ግዙፍ ፕሮጀክት የጨረታ ውጤት ሲለጠፍ፣ አሸናፊው ሩቅ አልነበረም። ያው "የህዝቡን ቪላ" አበርካች፣ የዘመናችን ሩህሩህ ቱጃር ሆነው እርፍ አሉ!
ይሄን ጊዜ ሌሎቹ ተጫራቾች… ማለትም ጨረታ በወረቀት፣ በማህተምና በፊርማ ብቻ የሚሸነፍ የሚመስላቸው የዋሃን ነጋዴዎች… አንጀታቸው አረረ። “እንዴት እርሳቸው ያሸንፋሉ? የእኛ ዋጋ እኮ በጣም አነስተኛ ነበር! የቴክኒክ ሰነዳችንም ቢሆን ከአውሮፓ ስታንዳርድ የሚስተካከል ነበር!” በማለት የጨረታ ኮሚቴውን አፍጠው ጠየቁ።
ኮሚቴው መልስ ቢያጣ፣ ጉዳዩ ወደ ክቡር ሚኒስትሩ ጆሮ ደረሰ። ሚኒስትሩ ግን ይህን ሲሰሙ ከመቆጣት ይልቅ፣ እንደ አንድ ሩቅ አላሚ "ልማታዊ አባት" ፈገግ አሉ። የተወሰኑትን ተጫራቾች ቢሯቸው አስጠርተው በለዘበ አንደበት እንዲህ ሲሉ የጨረታውን ስነ-መለኮት አስረዷቸው፡-
“እህህ... እናንተ ሰዎች ግብዞች ናችሁ፣ ፊደል እንጂ አገር አላነበባችሁም! የጨረታ ሰነድ ማለት እኮ በወረቀት ላይ የተጻፈ የውሸት ተስፋ ነው። እናንተ 'ነገ እንገነባለን፣ አቅሙ አለን፣ እናደርጋለን' ብላችሁ በባዶ ወረቀት ስታነበንቡ፣ አቶ [እገሌ] ግን ማታ አስቦ፣ ጧት ጂ-ፕላስ-ስሪ ቪላ አሰርቶ፣ ከነሙሉ ዕቃው ቁልፍ የሚያስረክብ 'የተግባር ሰው' መሆኑን ለህዝብ (ማለትም ለእኔ) በተጨባጭ አሳይቷል። ታዲያ ሀገር የምትለወጠው በወረቀት ቃል ኪዳን ነው ወይስ በተጨባጭ አቅርቦት?”
ተጫራቾቹ አንገታቸውን ደፉ። እውነትም መመዘኛውን አልተረዱትም ነበር። አቶ [እገሌ] የተባሉት ባለሃብት ጨረታውን ያሸነፉት "በቴክኒክ እና በፋይናንስ" ብቃት ሳይሆን፣ "በቅድመ-ክፍያ እና በፍቅር" ብቃት እንደሆነ አሁን ገባቸው። ደግሞም እኮ የአቶ እገሌ ሰነድ ከሌሎቹ የሚለየው በኮምፒውተር ታይፕ የተመታ ሳይሆን፣ በብሎኬት እና በኮንክሪት የታነጸ መሆኑ ነው።
ሚኒስትሩ ንግግራቸውን ሲያጠቃልሉ፣ “አቶ እገሌ ለዚህ መሥሪያ ቤት ያሳዩት 'የማስረከብ ፍጥነት' ወደር የሌለው ነው። ትናንት ማታ ቃል የገቡትን ቪላ... ይቅርታ ፕሮጀክት፣ ወዲያው ነው እጄ ላይ ያስቀመጡት። ስለዚህ የህዝቡን ፕሮጀክት ከእርሳቸው የተሻለ ማንም አያሳካውም!” በማለት በጭብጨባ አሰናበቷቸው።
በእርግጥም በሀገራችን የጨረታ ሳጥን የሚከፈተው በሰም እና በታሸገ ኤንቨሎፕ አይደለም፤ የጨረታ ሳጥን የሚከፈተው በቪላ በር ቁልፍ ነው! "የሰጠህን አብላው፣ የቀበጠህን አባርረው" የሚለው የቀድሞ አባቶቻችን ጥልቅ ፍልስፍና በዘመናዊው ቢሮክራሲ ውስጥ ሲተረጎም እንዲህ ያምራል። ባለሃብቱ ቤቱን ለህዝብ ሰጡ፣ ሚኒስትሩ ደግሞ የህዝቡን ፕሮጀክት ለባለሃብቱ ሰጡ። ፍትሃዊ የሀብት ክፍፍል ማለት ይሄው አይደል?
አበጀ በለው የላኩልን
24 days ago
"ከአሁን በኋላ መንገድ ላይ ጉድጓድ
ካየሁ ኮንትራክተሩ ያልቅለታል!"
የኡጋንዳው ታዋቂ ጄኔራል ሙሆዚ ካይነሩጋባ በሙስና በተዘፈቁ የመንገድ ተቋራጮች ላይ ጠንካራ እርምጃ እንደሚወስዱ ዝተዋል። "የመንገድ ግንባታ ክፍያ ከፍለን ካበቃን በኋላ በመንገዱ ላይ አንድም ጉድጓድ ካየሁ፣ ያ ኮንትራክተር በህይወቱ ይከፍላል" ሲሉ ባለሙሉ ስልጣኑ ጄኔራል በይፋ አስታውቀዋል።
seledadotio
seledadotio
ካየሁ ኮንትራክተሩ ያልቅለታል!"
የኡጋንዳው ታዋቂ ጄኔራል ሙሆዚ ካይነሩጋባ በሙስና በተዘፈቁ የመንገድ ተቋራጮች ላይ ጠንካራ እርምጃ እንደሚወስዱ ዝተዋል። "የመንገድ ግንባታ ክፍያ ከፍለን ካበቃን በኋላ በመንገዱ ላይ አንድም ጉድጓድ ካየሁ፣ ያ ኮንትራክተር በህይወቱ ይከፍላል" ሲሉ ባለሙሉ ስልጣኑ ጄኔራል በይፋ አስታውቀዋል።
seledadotio
seledadotio
25 days ago
በሙስና የወንጀል ድርጊት የተከሰሱ በእስራት ተቀጡ
በፌዴሬሽን ምክር ቤት የሕገ መንግሥት ጉዳዮች የቀድሞ ዳይሬክተርን ጨምሮ 7 ግለሰቦች በተከሰሱበት የማይገባ ጥቅምን በማግኘት የወንጀል ድርጊት በእስራት ተቀጡ።
ግለሰቦቹ በዜግነት ኤርትራዊት የሆነች ግለሰብ ኢትዮጵያዊት ናት በማለት 400 ሚሊየን ብር የሚገመት ቤት እንድታገኝ ለማድረግ በመደራደራቸው ከ2 እስከ 7 ዓመት በሚደረስ ጽኑ እስራት እና በገንዘብ ቅጣት ተቀጥተዋል፡፡
ተከሳሾች 1ኛ አቶ ሙልዬ ወለላው የፌዴሬሽን ም/ቤት የህገ መንግሥት ትርጉምና የሕጎች ሕገ መንግሥታዊነት ክትትል ጉዳዮች ዳይሬክተር የነበረ፣ 2ኛ አቶ ኃ/ሚካኤል ልኬ የህግ አማካሪ እና ጠበቃ፣ 3ኛ አቶ ቃላት ባህታ በግል ስራ የሚተዳደርን ጨምሮ 7 ግለሰቦች ናቸው፡፡
በመጀመሪያ ክስ በ1ኛ፣ 2ኛ እና 3ኛ ተከሳሾች ላይ የቀረበ ሲሆን በ1996 ዓ.ም የወጣውን የወንጀል ሕግ አንቀጽ 32(1) (ሀ)፣ 33 እና የሙስና ወንጀሎችን ለመደንገግ የወጣውን አዋጅ ቁጥር 881/2007 አንቀጽ 9 (1) (ሀ) እና (2) ስር የተመለከተውን በመተላለፍ ነው፡፡
1ኛ ተከሳሽ ከ2ኛ እና 3ኛ ተከሳሾች ጋር በመመሳጠር የማይገባቸውን ጥቅም ለራሳቸው ለማግኘትና ለሌሎችም ለማስገኘት በማሰብ በኢትዮጵያና ኤርትራ መካከል ተከስቶ የነበረውን ግጭት ተከትሎ የሀገር ደህንነትን እና ህልውናን ለማስጠበቅ ሲባል ከሀገር የተሸኙ ኤርትራዊያን ንብረቶችን በጨረታ እንዲሸጥ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በሰጠው ትዕዛዝ መሰረት ከሀገር እንዲወጡ በተደረጉት ኤርትራዊ ቦሌ ክ/ከ ወረዳ 3 ስር የሚገኝ መኖርያ ቤት እና ይዞታ ለጨረታ እንዲቀርብ ተደርጎ 1ኛ የዐቃቤ ህግ ምስክር ወ/ሮ አልጋነሽ ኃይሉ የጨረታው አሸናፊ በመሆን በ1992 ዓ.ም የሽያጭ ውል በመፈፀም ቤቱን ከተረከቡ በኋላ ተከሳሾች በሀሰተኛ ደብዳቤው መነሻነት በዜግነት ኤርትራዊት የሆነችው 4ኛ ተከሳሽ ኢትዮጵያዊ ናት በሚል መደምደሚያ ላይ በመድረስ ውሉ ፈርሶ ቤቱን ወ/ሮ አልጋነሽ ኃይሉ ኤርትራዊት ለሆነችው 4ኛ ተከሳሽ ወ/ሮ ኤልሳቤት ተስፋጽዮን እንድታስረክብ በማለት የፌዴሬሽን ም/ቤት የወሰነውን ውሳኔ ድጋሚ ለምክር ቤቱ እንዳይቀርብ ለማድረግ በአካልና በስልክ በመገናኘትና በመደራደር፣ የዐቃቤ ህግ 1ኛ ምስክር ብር 400 ሚሊየን የሚገመት ቤትን እንዲያጡ አድርገዋል፡፡
በዚህም በዋና ወንጀል አድራጊነት በፈፀሙት ስልጣንን ያለአግባብ መገልገል ከባድ የሙስና ወንጀል መፈጸማቸውን ዐቃቤ ሕግ በክሱ ላይ ዘርዝሯል።
በሁተለኛ ክስ በተመሳሳይ1ኛ፣ 2ኛ፣ 5ኛ እና 6ኛ ተከሳሾች ከላይ በዝርዝር በተገለጸው የወንጀል ድርጊታቸው በህገ መንግሥት አጣሪ ጉባኤ በአብላጫው ድምጽ ትርጉም አያስፈልገውም በማለት በመወሰኑ በውሳኔው ቅር በመሰኘት የህገ መንግሥት ትርጉም ይሰጥልኝ ሲሉ ሕገ መንግሥት ትርጉም እንዲሰጣቸው ለፌዴሬሽን ም/ቤት የዕግድ እና የይግባኝ አቤቱታ በም/ቤቱ ተቀባይነት አግኝቶ ውሳኔው እንዳይቀየር በማድረግ ከፍተኛ ጥቅም ለማግኘት እና የግል ተበዳዮችን ይዞታ በማሳጣት ከፍተኛ የገንዘብ ጉዳት በማድረሳቸው 1ኛ እና 6ኛ ተከሳሾች በመንግሥት ወይም ህዝባዊ ድርጅት ሰራተኞች ብቻ በሚፈጸም የሙስና ወንጀል ውስጥ በልዩ ወንጀል አድራጊነት ተካፋይ ከሆኑት 2ኛ እና 5ኛ ተከሳሾች ጋር በዋና ወንጀል አድራጊነት ተካፋይ በመሆን በፈጸሙት የከባድ የስልጣን ያለአግባብ መገልገል ወንጀል ተከሰዋል፡፡
በሶስተኛ ክስ በ1ኛ እና 7ኛተከሳሾች 1ኛ ተከሳሽ በተጨማሪነት ለራሱም የማይገባውን 200 ሺህ ብር በማግኘቱ 1ኛ ተከሳሽ በመንግሥት ወይም ህዝባዊ ድርጅት ሰራተኞች ብቻ በሚፈጸም የሙስና ወንጀል ውስጥ በልዩ ወንጀል አድራጊነት ተካፋይ ከሆነው 7ኛ ተከሳሽ ጋር በዋና ወንጀል አድራጊነት ተካፋይ በመሆን በፈጸሙት በከባድ ስልጣንን አላግባብ መገልገል የሙስና ወንጀል የቅጣት ውሳኔ ተላልፎባቸዋል፡፡
ተከሳሾች ዛሬ የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 4ኛ የሙስና ጉዳዮች ወንጀል ችሎት በዋለዉ ችሎት 1ኛ ተከሳሽ በ6 ዓመት ከ4 ወር ጽኑ እስራት እና 3 ሺህ ብር፣ 2ኛ ተከሳሽ 2 ዓመት ከ8 ወር እና 5 ሺህ ብር፣ 3ኛ ተከሳሽ በቂ ማስረጃ ስላልተገኘበት በነጻ፣ 4ኛ ተከሳሽ 4 ዓመት ከ6 ወር፣ 5ኛ እና 6ኛ ተከሳሽ 2 ዓመት ከ8 ወር እና 1 ሺህ ብር እንዲሁም 7ኛ ተከሳሽ 7 ዓመት ከ6 ወር እና 10 ሺህ ብር እንዲቀጡ ወስኗል።
FBC
በፌዴሬሽን ምክር ቤት የሕገ መንግሥት ጉዳዮች የቀድሞ ዳይሬክተርን ጨምሮ 7 ግለሰቦች በተከሰሱበት የማይገባ ጥቅምን በማግኘት የወንጀል ድርጊት በእስራት ተቀጡ።
ግለሰቦቹ በዜግነት ኤርትራዊት የሆነች ግለሰብ ኢትዮጵያዊት ናት በማለት 400 ሚሊየን ብር የሚገመት ቤት እንድታገኝ ለማድረግ በመደራደራቸው ከ2 እስከ 7 ዓመት በሚደረስ ጽኑ እስራት እና በገንዘብ ቅጣት ተቀጥተዋል፡፡
ተከሳሾች 1ኛ አቶ ሙልዬ ወለላው የፌዴሬሽን ም/ቤት የህገ መንግሥት ትርጉምና የሕጎች ሕገ መንግሥታዊነት ክትትል ጉዳዮች ዳይሬክተር የነበረ፣ 2ኛ አቶ ኃ/ሚካኤል ልኬ የህግ አማካሪ እና ጠበቃ፣ 3ኛ አቶ ቃላት ባህታ በግል ስራ የሚተዳደርን ጨምሮ 7 ግለሰቦች ናቸው፡፡
በመጀመሪያ ክስ በ1ኛ፣ 2ኛ እና 3ኛ ተከሳሾች ላይ የቀረበ ሲሆን በ1996 ዓ.ም የወጣውን የወንጀል ሕግ አንቀጽ 32(1) (ሀ)፣ 33 እና የሙስና ወንጀሎችን ለመደንገግ የወጣውን አዋጅ ቁጥር 881/2007 አንቀጽ 9 (1) (ሀ) እና (2) ስር የተመለከተውን በመተላለፍ ነው፡፡
1ኛ ተከሳሽ ከ2ኛ እና 3ኛ ተከሳሾች ጋር በመመሳጠር የማይገባቸውን ጥቅም ለራሳቸው ለማግኘትና ለሌሎችም ለማስገኘት በማሰብ በኢትዮጵያና ኤርትራ መካከል ተከስቶ የነበረውን ግጭት ተከትሎ የሀገር ደህንነትን እና ህልውናን ለማስጠበቅ ሲባል ከሀገር የተሸኙ ኤርትራዊያን ንብረቶችን በጨረታ እንዲሸጥ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በሰጠው ትዕዛዝ መሰረት ከሀገር እንዲወጡ በተደረጉት ኤርትራዊ ቦሌ ክ/ከ ወረዳ 3 ስር የሚገኝ መኖርያ ቤት እና ይዞታ ለጨረታ እንዲቀርብ ተደርጎ 1ኛ የዐቃቤ ህግ ምስክር ወ/ሮ አልጋነሽ ኃይሉ የጨረታው አሸናፊ በመሆን በ1992 ዓ.ም የሽያጭ ውል በመፈፀም ቤቱን ከተረከቡ በኋላ ተከሳሾች በሀሰተኛ ደብዳቤው መነሻነት በዜግነት ኤርትራዊት የሆነችው 4ኛ ተከሳሽ ኢትዮጵያዊ ናት በሚል መደምደሚያ ላይ በመድረስ ውሉ ፈርሶ ቤቱን ወ/ሮ አልጋነሽ ኃይሉ ኤርትራዊት ለሆነችው 4ኛ ተከሳሽ ወ/ሮ ኤልሳቤት ተስፋጽዮን እንድታስረክብ በማለት የፌዴሬሽን ም/ቤት የወሰነውን ውሳኔ ድጋሚ ለምክር ቤቱ እንዳይቀርብ ለማድረግ በአካልና በስልክ በመገናኘትና በመደራደር፣ የዐቃቤ ህግ 1ኛ ምስክር ብር 400 ሚሊየን የሚገመት ቤትን እንዲያጡ አድርገዋል፡፡
በዚህም በዋና ወንጀል አድራጊነት በፈፀሙት ስልጣንን ያለአግባብ መገልገል ከባድ የሙስና ወንጀል መፈጸማቸውን ዐቃቤ ሕግ በክሱ ላይ ዘርዝሯል።
በሁተለኛ ክስ በተመሳሳይ1ኛ፣ 2ኛ፣ 5ኛ እና 6ኛ ተከሳሾች ከላይ በዝርዝር በተገለጸው የወንጀል ድርጊታቸው በህገ መንግሥት አጣሪ ጉባኤ በአብላጫው ድምጽ ትርጉም አያስፈልገውም በማለት በመወሰኑ በውሳኔው ቅር በመሰኘት የህገ መንግሥት ትርጉም ይሰጥልኝ ሲሉ ሕገ መንግሥት ትርጉም እንዲሰጣቸው ለፌዴሬሽን ም/ቤት የዕግድ እና የይግባኝ አቤቱታ በም/ቤቱ ተቀባይነት አግኝቶ ውሳኔው እንዳይቀየር በማድረግ ከፍተኛ ጥቅም ለማግኘት እና የግል ተበዳዮችን ይዞታ በማሳጣት ከፍተኛ የገንዘብ ጉዳት በማድረሳቸው 1ኛ እና 6ኛ ተከሳሾች በመንግሥት ወይም ህዝባዊ ድርጅት ሰራተኞች ብቻ በሚፈጸም የሙስና ወንጀል ውስጥ በልዩ ወንጀል አድራጊነት ተካፋይ ከሆኑት 2ኛ እና 5ኛ ተከሳሾች ጋር በዋና ወንጀል አድራጊነት ተካፋይ በመሆን በፈጸሙት የከባድ የስልጣን ያለአግባብ መገልገል ወንጀል ተከሰዋል፡፡
በሶስተኛ ክስ በ1ኛ እና 7ኛተከሳሾች 1ኛ ተከሳሽ በተጨማሪነት ለራሱም የማይገባውን 200 ሺህ ብር በማግኘቱ 1ኛ ተከሳሽ በመንግሥት ወይም ህዝባዊ ድርጅት ሰራተኞች ብቻ በሚፈጸም የሙስና ወንጀል ውስጥ በልዩ ወንጀል አድራጊነት ተካፋይ ከሆነው 7ኛ ተከሳሽ ጋር በዋና ወንጀል አድራጊነት ተካፋይ በመሆን በፈጸሙት በከባድ ስልጣንን አላግባብ መገልገል የሙስና ወንጀል የቅጣት ውሳኔ ተላልፎባቸዋል፡፡
ተከሳሾች ዛሬ የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 4ኛ የሙስና ጉዳዮች ወንጀል ችሎት በዋለዉ ችሎት 1ኛ ተከሳሽ በ6 ዓመት ከ4 ወር ጽኑ እስራት እና 3 ሺህ ብር፣ 2ኛ ተከሳሽ 2 ዓመት ከ8 ወር እና 5 ሺህ ብር፣ 3ኛ ተከሳሽ በቂ ማስረጃ ስላልተገኘበት በነጻ፣ 4ኛ ተከሳሽ 4 ዓመት ከ6 ወር፣ 5ኛ እና 6ኛ ተከሳሽ 2 ዓመት ከ8 ወር እና 1 ሺህ ብር እንዲሁም 7ኛ ተከሳሽ 7 ዓመት ከ6 ወር እና 10 ሺህ ብር እንዲቀጡ ወስኗል።
FBC
27 days ago
በአሜሪካ የፖለቲካ ትኩሳት የፈጠረው የ1.776 ቢሊዮን ዶላር የካሳ ፈንድ ጉዳይ
#ethiopia | የአሜሪካ ፍትህ ሚኒስቴር ባለፈው የጆ ባይደን የፕሬዝዳንትነት ዘመን "በፖለቲካ ምክንያት ጥቃት ደርሶብናል" ለሚሉ የዶናልድ ትራምፕ ደጋፊዎችና የቅርብ አጋሮች የሚከፈል የ1.776 ቢሊዮን ዶላር ፈንድ ማቋቋሙን አስታውቋል።
የአሜሪካን የነፃነት አዋጅ መታሰቢያ ዓመተ-ምህረትን በመውሰድ "የፀረ-መንግስት መሳሪያነት" የተሰኘው ይህ ፈንድ ይፋ ሊሆን የቻለው፣ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በግል ማንነታቸው በገቢዎች ባለስልጣን ላይ የመሰረቱትን የ10 ቢሊዮን ዶላር ክስ በፈቃደኝነት ማቋረጣቸውን ተከትሎ ነው።
በተደረገው ስምምነት መሰረት ለፕሬዝዳንት ትራምፕ ምንም አይነት ቀጥተኛ የገንዘብ ክፍያ የማይፈጸምላቸው ቢሆንም፣ የሀገሪቱ ፍትህ ሚኒስቴር ግን ለፕሬዝዳንቱ ይፋዊ የይቅርታ ደብዳቤ ያቀርባል።
የፍትህ ሚኒስቴር ጊዜያዊ ዋና አቃቤ ህግ እና የቀድሞው የትራምፕ የግል ጠበቃ ቶድ ብላንች በመግለጫቸው፤ የመንግስት መዋቅር በዜጎች ላይ እንደ ፖለቲካ መሳሪያ መሆን እንደሌለበትና ፈንዱ ቀደም ሲል የተፈጸሙ ስህተቶችን ለማረም የተዘረጋ ህጋዊ አሰራር መሆኑን አብራርተዋል።
ከታክስ ከፋዮች ህዝብ ገንዘብ የሚሸፈነውንና ይህንን ፈንድ የሚያስተዳድረውን ባለ አምስት አባላት ኮሚሽን ፕሬዝዳንት ትራምፕ የመሻርና የማባረር ሙሉ ስልጣን ያላቸው ሲሆን፣ የይገባኛል ጥያቄ ማቅረቢያው ጊዜ እስከ ታህሳስ 15 ቀን 2028 ዓ.ም ድረስ ክፍት ሆኖ ይቆያል።
ይህ ከዚህ ቀደም ታይቶ የማይታወቅ እርምጃ ትራምፕ በገዛ እጃቸው በሚቆጣጠሩት የመንግስት ተቋም በኩል ለደጋፊዎቻቸው ክፍያ እንዲፈጽሙ የሚያስችል በመሆኑ፣ በዴሞክራቶችና በሙስና መከላከል ተሟጋቾች ዘንድ ከፍተኛ ትችትና ህጋዊ ክስ ሊገጥመው እንደሚችል ተነግሯል።
ትራምፕ ክሳቸውን ከመተውታቸው ጥቂት ደቂቃዎች በፊት 100 የሚሆኑ የኮንግረስ ዴሞክራቶች ለፍርድ ቤት ባስገቡት ሰነድ፤ ፕሬዝዳንቱ የግል ጥቅምን ማስከበር ላይ ያተኮረ ግልጽ አድሎአዊ አሰራር እየፈጸሙ ነው ሲሉ ከሰዋል።
ይህ አዲስ ስምምነት እንደ ማይክል ፍሊን እና ካርተር ፔጅ ያሉ የትራምፕ የቅርብ አጋሮች ከዚህ ቀደም ከፍትህ ሚኒስቴር ጋር ካደረጓቸው የሚሊዮን ዶላር የካሳ ስምምነቶች ቀጥሎ የተመዘገበ ሌላኛው አነጋጋሪ ክስተት ሆኗል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን) #getutemesgen #getu
#trump #usa #justicedepartment #compensationfund #uspolitics #ethiopia
#ethiopia | የአሜሪካ ፍትህ ሚኒስቴር ባለፈው የጆ ባይደን የፕሬዝዳንትነት ዘመን "በፖለቲካ ምክንያት ጥቃት ደርሶብናል" ለሚሉ የዶናልድ ትራምፕ ደጋፊዎችና የቅርብ አጋሮች የሚከፈል የ1.776 ቢሊዮን ዶላር ፈንድ ማቋቋሙን አስታውቋል።
የአሜሪካን የነፃነት አዋጅ መታሰቢያ ዓመተ-ምህረትን በመውሰድ "የፀረ-መንግስት መሳሪያነት" የተሰኘው ይህ ፈንድ ይፋ ሊሆን የቻለው፣ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በግል ማንነታቸው በገቢዎች ባለስልጣን ላይ የመሰረቱትን የ10 ቢሊዮን ዶላር ክስ በፈቃደኝነት ማቋረጣቸውን ተከትሎ ነው።
በተደረገው ስምምነት መሰረት ለፕሬዝዳንት ትራምፕ ምንም አይነት ቀጥተኛ የገንዘብ ክፍያ የማይፈጸምላቸው ቢሆንም፣ የሀገሪቱ ፍትህ ሚኒስቴር ግን ለፕሬዝዳንቱ ይፋዊ የይቅርታ ደብዳቤ ያቀርባል።
የፍትህ ሚኒስቴር ጊዜያዊ ዋና አቃቤ ህግ እና የቀድሞው የትራምፕ የግል ጠበቃ ቶድ ብላንች በመግለጫቸው፤ የመንግስት መዋቅር በዜጎች ላይ እንደ ፖለቲካ መሳሪያ መሆን እንደሌለበትና ፈንዱ ቀደም ሲል የተፈጸሙ ስህተቶችን ለማረም የተዘረጋ ህጋዊ አሰራር መሆኑን አብራርተዋል።
ከታክስ ከፋዮች ህዝብ ገንዘብ የሚሸፈነውንና ይህንን ፈንድ የሚያስተዳድረውን ባለ አምስት አባላት ኮሚሽን ፕሬዝዳንት ትራምፕ የመሻርና የማባረር ሙሉ ስልጣን ያላቸው ሲሆን፣ የይገባኛል ጥያቄ ማቅረቢያው ጊዜ እስከ ታህሳስ 15 ቀን 2028 ዓ.ም ድረስ ክፍት ሆኖ ይቆያል።
ይህ ከዚህ ቀደም ታይቶ የማይታወቅ እርምጃ ትራምፕ በገዛ እጃቸው በሚቆጣጠሩት የመንግስት ተቋም በኩል ለደጋፊዎቻቸው ክፍያ እንዲፈጽሙ የሚያስችል በመሆኑ፣ በዴሞክራቶችና በሙስና መከላከል ተሟጋቾች ዘንድ ከፍተኛ ትችትና ህጋዊ ክስ ሊገጥመው እንደሚችል ተነግሯል።
ትራምፕ ክሳቸውን ከመተውታቸው ጥቂት ደቂቃዎች በፊት 100 የሚሆኑ የኮንግረስ ዴሞክራቶች ለፍርድ ቤት ባስገቡት ሰነድ፤ ፕሬዝዳንቱ የግል ጥቅምን ማስከበር ላይ ያተኮረ ግልጽ አድሎአዊ አሰራር እየፈጸሙ ነው ሲሉ ከሰዋል።
ይህ አዲስ ስምምነት እንደ ማይክል ፍሊን እና ካርተር ፔጅ ያሉ የትራምፕ የቅርብ አጋሮች ከዚህ ቀደም ከፍትህ ሚኒስቴር ጋር ካደረጓቸው የሚሊዮን ዶላር የካሳ ስምምነቶች ቀጥሎ የተመዘገበ ሌላኛው አነጋጋሪ ክስተት ሆኗል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን) #getutemesgen #getu
#trump #usa #justicedepartment #compensationfund #uspolitics #ethiopia
28 days ago
ሰላም፤ እንደምን አደራችሁ?
በሀገራችን የዴሞክራሲ ሥርዓት እንዲገነባና ባህል እንዲሆን ምርጫን ብቻ የመንግሥት ማቋቋሚያ አማራጭ አድርጎ መጠቀም የግድ ይላል። ኢትዮጵያ ምርጫን ብቸኛ አማራጭ ለማድረግ የቅርብ ጊዜ ልምምድ ብቻ ነው ያላት። ያውም የዘንድሮው ምርጫ ገና 7ኛዋ ልምምድ ነው። ልምምዱን ከወትሮዎቹ የተሻለ ባህል ለማድረግ ደግሞ ተቋማትን መፍጠር የግድ ይላል፡፡ የዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ደግሞ በሕዝቦች የነቃ ተሳትፎ፣ በፖለቲካ ፓርቲዎች እና በመንግሥት ትብብር የሚከናወን ሂደት ነው። ይህ ባህልም በሰዎች የአመለካከት እና የአስተሳሰብ ለውጥን በማምጣት ሀገርን ለመገንባት ያግዛል፡፡ ባህሉን መገንባት የሚያስፈልገው ሁሉም ዜጎች እኩል ተሳትፎ እንዲኖራቸው፣ በጋራ ጉዳዮች ላይ የአስተሳሰብና የተግባር ለውጥ እንዲመጣ ነው፡፡
የዴሞክራሲ ባህል እንዲገነባ ምርጫ ያስፈልጋል። ይህንን እውን ለማድረግ የመንግሥት መዋቅር፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የማህበራት እና የሚዲያዎች ሚናም ወሳኝ ናቸው፡፡
የመንግሥት መዋቅር የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታን እንደ ማዕከል ለማስተባበር ያግዛል፡፡ የፖለቲካ ፓርቲዎች በተሳትፏቸው ለሀገር የሚጠቅሙ ስትራቴጂካዊ ጉዳዮችን በማመንጨት ወሳኝ ናቸው፡፡ ማህበራት ደግሞ በየአደረጃጀቶቻቸው የለውጥ ተሳትፎ በማድረግ በዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ያግዛሉ፡፡
የሚዲያ ተቋማት በሙያዊ ሥነምግባር እና በሕግ በመመራት እውነተኛ መረጃን ለህዝብ በማቅረብ የዴሞክራሲ ባህልን ግንባታን ያሳልጣሉ፡፡ በድምሩ እነዚህ ተቋማት በትብብር እና በቅንጅት በመስራት የዴሞክራሲ ባህልን ለመገንባት ያግዛሉ።
ህዝብም ለሀገር ግንባታ የሚጠቅሙ አስተሣሰቦችን በማራመድ አበርክቶው ከፍተኛ ይሆናል፡፡ በፖለቲካ ሂደት ላይም የነቃ ተሳትፎ በማድረግ ዴሞክራሲን ይገነባል፡፡
ባህሉን ለመገንባት ተቋማትን መፍጠር የግድ ይላል፡፡ ጠንካራ፣ ውጤታማ እና ዘላቂነት ያላቸውን ድርጅቶች ወይም መዋቅሮችን መፍጠር ለአንድ ማህበረሰብ ወይም ሀገር ወሳኝ ነው፡፡
የኢኮኖሚ፣ የፖለቲካ እና የማህበራዊ እድገትን ለማረጋገጥ ስለሚረዱ፡፡ ተቋማት ግንባታ በአጠቃላይ በግልጽ ራዕይ እና ተልዕኮ፣ ህጋዊ መዋቅር፣የሰው ኃይል ልማት፣ በቴክኖሎጂ የዘመነ አሰራር፣ ግልጽነትንና ተጠያቂነት ፣ቀጣይነትን፣ የተሻሻለ አገልግሎት፣ እምነት የተገነባበት እና ኢንቨስትመንት የሚሳብበት እንዲሆን ያስችላል፡፡
ከተቋማትም የዴሞክራሲ ተቋማትን መገንባት ደግሞ የሕግ የበላይነትን ለማረጋገጥ፣ ሰብአዊ መብቶችን ለማስከበር እና የዜጎችን እኩል ተሳትፎ ለማረጋገጥ ወሳኝ ነው። እነዚህ ተቋማት ገለልተኛ ናቸው፡፡ ይህ አሰራርም ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ግንባር ቀደም ሚና እንዲጫወቱ ያደርጋል፡፡
በዚህ ረገድ ምን ምን ሥራዎች ተሠሩ?
1. በዴሞክራሲ ተቋማት ግንባታ የምርጫ ቦርድ ሚና ከፍተኛ ነው፡፡ ነፃ፣ ገለልተኛ፣ ዴሞክራሲያዊ እና እውነተኛ ምርጫን ለማካሄድ ያስችላል፡፡ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድም በዚሁ መሠረት የ7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ለማካሄድ ሚናውን እየተወጣ ይገኛል፡፡ የምርጫ ቦርድ ተግባር የስልጣን ምንጭ የህዝብ ድምጽ ይሁንታ እንጂ ጠብ መንጃ ያለመሆኑን ያረጋግጣል።
2. ገለልተኛ የፍትሕ ተቋማት ተገንብተው ፍርድ ቤቶች እና የሕግ አስከባሪ አካላት በነጻነት እንዲሰሩ ተደርጓል፡፡ በምርጫ ወቅትም በነጻነት ክትትል በማድረግ ያለ አድልዎ በማገልገል የሂደቱን ዴሞክራሲያዊነት ያረጋግጣሉ።
3. የሰብአዊ መብት ኮሚሽን ነጻ ሆኖ የመብት ጥሰቶችን በመከታተል እየተከላከለ፤ ለፍትሕና ርትዕ እየሰራ ይገኛል፡፡ ይህንንም ማረጋገጥ ተችሏል።
4. የዕንባ ጠባቂ ተቋም የመልካም አስተዳደር እጥረቶች እና የሙስና ጉዳዮችን በመመርመር በገለልተኛነት ለሀቅ ይሰራል፡፡
5. መገናኛ ብዙኃን ነፃ ሆነው ለሕዝብ ትክክለኛ መረጃ እንዲያደርሱ በተሰራው የተቋማት ግንባታ ሪፎርም እውን ሆኗል፡፡ በህዝብ እና በመንግሥት መካከል ሚዛናዊ የመረጃ ድልድይ በመሆንም የመንግሥትን አሰራር ፈትሸው የሚታረመው እንዲስተካከል፤ የሚበረታታው ሞዴል እንዲሆን በማሳየት ያቀርባሉ፡፡
6. የፀጥታ ተቋማት ገለልተኛ ሆነው እንዲገነቡ፣ ሁሉንም እኩል እንዲያገለግሉ፣ ከግለሰብ እና ከፓርቲ በላይ ለሀገር ህልውና እንዲቆሙ ተደርገዋል።
እንደነዚህ አይነት ተቋማትን መገንባት የስልጣን ሚዛንን ለመጠበቅ፣ ተጠያቂነትን ለማስፈን፣ ግልጽነትን ለመፍጠር፣ የዜጎችን እምነትና ተሳትፎ ለማሳደግ ይረዳሉ፡፡
በሕግ አውጪ፣ ተርጓሚ እና አስፈጻሚ መካከል የስልጣን ሚዛንን በመጠበቅ ቁጥጥር ያደርጋሉ፡፡ የመንግሥት ባለሥልጣናት ለሚሰጡት ውሳኔ ተጠያቂ መሆናቸውን በማረጋገጥ የመንግሥት አሰራር ለሕዝብ ክፍት እና ግልጽ እንዲሆን ያደርጋሉ፡፡ ሕዝቡም በሕግ እና በአስተዳደር ሥርዓቱ ላይ እምነት እንዲኖረው ያስችላሉ፡፡
በመሆኑም መንግሥት የዴሞክራሲ ባህልን ለመገንባት ተቋማትን መገንባት የግድ ነው ብሎ ስላመነ በርካታ ስራዎችን ሰርቷል፡፡ የመጀመሪያው የወሰደው የፖለቲካ ቁርጠኝነት ነው፡፡ ቁርጠኛ በመሆንም የሕግ ማሻሻያዎችን በማድረግ ነጻና ገለልተኛ ተቋማት እንዲፈጠሩ አድርጓል፡፡ ይህም ሥራቸውን ያለጣልቃገብነት እንዲከውኑ አግዟቸዋል፡፡ የፋይናንስ፣ የሎጂስቲክስ እና የሰው ኃይል ነጻነት ኖሯቸው በገለልተኛ ሰራተኞች እንዲሰሩም እያደረገ ይገኛል፡፡
እስከ አሁን እንደ ሀገር ለዴሞክራሲ ባህል ግንባታ በርካታ ስራዎችን በጋራ ሰርተናል። የዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ደግሞ ሂደት በመሆኑ ቀጣይ ነው። ስለዚህ የባህሉ መገለጫ በሆነው የዘንድሮ ምርጫ ላይ ካርዳችንን በመጠቀም ይበጀናል የምንለውን ለመምረጥና ሀገር ለማሻገር ተዘጋጅተናል?
እንዘጋጅ! እንምረጥ! በጋራ ሀገር እናሻግር!
በሀገራችን የዴሞክራሲ ሥርዓት እንዲገነባና ባህል እንዲሆን ምርጫን ብቻ የመንግሥት ማቋቋሚያ አማራጭ አድርጎ መጠቀም የግድ ይላል። ኢትዮጵያ ምርጫን ብቸኛ አማራጭ ለማድረግ የቅርብ ጊዜ ልምምድ ብቻ ነው ያላት። ያውም የዘንድሮው ምርጫ ገና 7ኛዋ ልምምድ ነው። ልምምዱን ከወትሮዎቹ የተሻለ ባህል ለማድረግ ደግሞ ተቋማትን መፍጠር የግድ ይላል፡፡ የዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ደግሞ በሕዝቦች የነቃ ተሳትፎ፣ በፖለቲካ ፓርቲዎች እና በመንግሥት ትብብር የሚከናወን ሂደት ነው። ይህ ባህልም በሰዎች የአመለካከት እና የአስተሳሰብ ለውጥን በማምጣት ሀገርን ለመገንባት ያግዛል፡፡ ባህሉን መገንባት የሚያስፈልገው ሁሉም ዜጎች እኩል ተሳትፎ እንዲኖራቸው፣ በጋራ ጉዳዮች ላይ የአስተሳሰብና የተግባር ለውጥ እንዲመጣ ነው፡፡
የዴሞክራሲ ባህል እንዲገነባ ምርጫ ያስፈልጋል። ይህንን እውን ለማድረግ የመንግሥት መዋቅር፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የማህበራት እና የሚዲያዎች ሚናም ወሳኝ ናቸው፡፡
የመንግሥት መዋቅር የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታን እንደ ማዕከል ለማስተባበር ያግዛል፡፡ የፖለቲካ ፓርቲዎች በተሳትፏቸው ለሀገር የሚጠቅሙ ስትራቴጂካዊ ጉዳዮችን በማመንጨት ወሳኝ ናቸው፡፡ ማህበራት ደግሞ በየአደረጃጀቶቻቸው የለውጥ ተሳትፎ በማድረግ በዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ያግዛሉ፡፡
የሚዲያ ተቋማት በሙያዊ ሥነምግባር እና በሕግ በመመራት እውነተኛ መረጃን ለህዝብ በማቅረብ የዴሞክራሲ ባህልን ግንባታን ያሳልጣሉ፡፡ በድምሩ እነዚህ ተቋማት በትብብር እና በቅንጅት በመስራት የዴሞክራሲ ባህልን ለመገንባት ያግዛሉ።
ህዝብም ለሀገር ግንባታ የሚጠቅሙ አስተሣሰቦችን በማራመድ አበርክቶው ከፍተኛ ይሆናል፡፡ በፖለቲካ ሂደት ላይም የነቃ ተሳትፎ በማድረግ ዴሞክራሲን ይገነባል፡፡
ባህሉን ለመገንባት ተቋማትን መፍጠር የግድ ይላል፡፡ ጠንካራ፣ ውጤታማ እና ዘላቂነት ያላቸውን ድርጅቶች ወይም መዋቅሮችን መፍጠር ለአንድ ማህበረሰብ ወይም ሀገር ወሳኝ ነው፡፡
የኢኮኖሚ፣ የፖለቲካ እና የማህበራዊ እድገትን ለማረጋገጥ ስለሚረዱ፡፡ ተቋማት ግንባታ በአጠቃላይ በግልጽ ራዕይ እና ተልዕኮ፣ ህጋዊ መዋቅር፣የሰው ኃይል ልማት፣ በቴክኖሎጂ የዘመነ አሰራር፣ ግልጽነትንና ተጠያቂነት ፣ቀጣይነትን፣ የተሻሻለ አገልግሎት፣ እምነት የተገነባበት እና ኢንቨስትመንት የሚሳብበት እንዲሆን ያስችላል፡፡
ከተቋማትም የዴሞክራሲ ተቋማትን መገንባት ደግሞ የሕግ የበላይነትን ለማረጋገጥ፣ ሰብአዊ መብቶችን ለማስከበር እና የዜጎችን እኩል ተሳትፎ ለማረጋገጥ ወሳኝ ነው። እነዚህ ተቋማት ገለልተኛ ናቸው፡፡ ይህ አሰራርም ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ግንባር ቀደም ሚና እንዲጫወቱ ያደርጋል፡፡
በዚህ ረገድ ምን ምን ሥራዎች ተሠሩ?
1. በዴሞክራሲ ተቋማት ግንባታ የምርጫ ቦርድ ሚና ከፍተኛ ነው፡፡ ነፃ፣ ገለልተኛ፣ ዴሞክራሲያዊ እና እውነተኛ ምርጫን ለማካሄድ ያስችላል፡፡ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድም በዚሁ መሠረት የ7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ለማካሄድ ሚናውን እየተወጣ ይገኛል፡፡ የምርጫ ቦርድ ተግባር የስልጣን ምንጭ የህዝብ ድምጽ ይሁንታ እንጂ ጠብ መንጃ ያለመሆኑን ያረጋግጣል።
2. ገለልተኛ የፍትሕ ተቋማት ተገንብተው ፍርድ ቤቶች እና የሕግ አስከባሪ አካላት በነጻነት እንዲሰሩ ተደርጓል፡፡ በምርጫ ወቅትም በነጻነት ክትትል በማድረግ ያለ አድልዎ በማገልገል የሂደቱን ዴሞክራሲያዊነት ያረጋግጣሉ።
3. የሰብአዊ መብት ኮሚሽን ነጻ ሆኖ የመብት ጥሰቶችን በመከታተል እየተከላከለ፤ ለፍትሕና ርትዕ እየሰራ ይገኛል፡፡ ይህንንም ማረጋገጥ ተችሏል።
4. የዕንባ ጠባቂ ተቋም የመልካም አስተዳደር እጥረቶች እና የሙስና ጉዳዮችን በመመርመር በገለልተኛነት ለሀቅ ይሰራል፡፡
5. መገናኛ ብዙኃን ነፃ ሆነው ለሕዝብ ትክክለኛ መረጃ እንዲያደርሱ በተሰራው የተቋማት ግንባታ ሪፎርም እውን ሆኗል፡፡ በህዝብ እና በመንግሥት መካከል ሚዛናዊ የመረጃ ድልድይ በመሆንም የመንግሥትን አሰራር ፈትሸው የሚታረመው እንዲስተካከል፤ የሚበረታታው ሞዴል እንዲሆን በማሳየት ያቀርባሉ፡፡
6. የፀጥታ ተቋማት ገለልተኛ ሆነው እንዲገነቡ፣ ሁሉንም እኩል እንዲያገለግሉ፣ ከግለሰብ እና ከፓርቲ በላይ ለሀገር ህልውና እንዲቆሙ ተደርገዋል።
እንደነዚህ አይነት ተቋማትን መገንባት የስልጣን ሚዛንን ለመጠበቅ፣ ተጠያቂነትን ለማስፈን፣ ግልጽነትን ለመፍጠር፣ የዜጎችን እምነትና ተሳትፎ ለማሳደግ ይረዳሉ፡፡
በሕግ አውጪ፣ ተርጓሚ እና አስፈጻሚ መካከል የስልጣን ሚዛንን በመጠበቅ ቁጥጥር ያደርጋሉ፡፡ የመንግሥት ባለሥልጣናት ለሚሰጡት ውሳኔ ተጠያቂ መሆናቸውን በማረጋገጥ የመንግሥት አሰራር ለሕዝብ ክፍት እና ግልጽ እንዲሆን ያደርጋሉ፡፡ ሕዝቡም በሕግ እና በአስተዳደር ሥርዓቱ ላይ እምነት እንዲኖረው ያስችላሉ፡፡
በመሆኑም መንግሥት የዴሞክራሲ ባህልን ለመገንባት ተቋማትን መገንባት የግድ ነው ብሎ ስላመነ በርካታ ስራዎችን ሰርቷል፡፡ የመጀመሪያው የወሰደው የፖለቲካ ቁርጠኝነት ነው፡፡ ቁርጠኛ በመሆንም የሕግ ማሻሻያዎችን በማድረግ ነጻና ገለልተኛ ተቋማት እንዲፈጠሩ አድርጓል፡፡ ይህም ሥራቸውን ያለጣልቃገብነት እንዲከውኑ አግዟቸዋል፡፡ የፋይናንስ፣ የሎጂስቲክስ እና የሰው ኃይል ነጻነት ኖሯቸው በገለልተኛ ሰራተኞች እንዲሰሩም እያደረገ ይገኛል፡፡
እስከ አሁን እንደ ሀገር ለዴሞክራሲ ባህል ግንባታ በርካታ ስራዎችን በጋራ ሰርተናል። የዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ደግሞ ሂደት በመሆኑ ቀጣይ ነው። ስለዚህ የባህሉ መገለጫ በሆነው የዘንድሮ ምርጫ ላይ ካርዳችንን በመጠቀም ይበጀናል የምንለውን ለመምረጥና ሀገር ለማሻገር ተዘጋጅተናል?
እንዘጋጅ! እንምረጥ! በጋራ ሀገር እናሻግር!
Sponsored by
Surafel
29 days ago
ነገ ግንቦት 10 ቀን 2018 ዓ.ም የመልሶ ግንባታ እና አቅም ማሳደግ እንዲሁም ቅድመ ጥገና ሥራ በአዲስ አበባ እና ሸገር ከተሞች የኃይል አቅርቦት ይቋረጣል፡፡
✅ከጠዋቱ 2:00 እስከ 9:00
👉በለገጣፎ፣ በሲዲሲ፣ በኮሰሮ፣ በኤሞሌስ ፋብሪካ፣ በካሰዴ፣ በጣፎ፣ በ44 ማዞሪያ ፣ በሰንዳፋ ጫፍ፤
✅ከጠዋቱ 2:30 እስከ 9:30
👉በወሰን ግሮሰሪ፣ በሲኤምሲ ሚካኤል፣ በካራሎ፣ በየካ አባዶ የጋራ መኖሪያ ቤቶች፣ በሸገር ዳቦ፣ በወይብላ ማርያም፣
👉በአውጉስታ፣ በአንፎ፣ በወይራ ሰፈር፣ በወይራ የጋራ መኖሪያ ቤቶች፣ በሞቢል ፣ በራሺያ ካምፕ፣ በተዘንአ ሆስፒታል ፣ በሙስና ሰፈር፣ በኮፊ ሲቲ አካባቢ፣ በኢነዲያና ት/ቤት አካባቢ፤
✅ከረፋዱ 3:00 እስከ 9:30
👉በማርቆስ መጋዘን ፣ በቀጨኔ 8 ቁጥር ማዞሪያ፣ በቀጨኔ 1ኛ፣ 2ኛ እና 3ኛ መንገድ ፣ በይመር ውሃ ፣ በመቀጠያ፣ በ19 ታቦት ማደሪያ፣ በመታፈሪ ሰፈር፣ በጴጥሮስ ሆስፒታል፣ በሽሮ ሜዳ፤
✅ከረፋዱ 3:00 እስከ ምሽቱ 12:00
👉በጀርመን ድልድይ ፣ በፈረንሳይ ኤምባሲ ወደ ጉራራ፣ በብሎኬት ገበያ፣ በኪዩር ሆስፒታል ፣ በራሳ ካሳ ክሊኒክ፣ በአቦ ቤተክርስቲያን፣ በእንጦጦ ኪዳነ-ምሕረት ቤተክርስቲያን፤
✅ከረፋዱ 4:00 እስከ 8:00
👉በቡልቡላ ሙሉውን ፣ በሳሪስ አቦ፣ በቡልቡላ ማርያም ማዞሪያ፤
✅ከረፋዱ 4:00 እስከ 9:00
👉በመሪ ኮንዶሚኒየም ፣ በአያት ዞን -1 እና ዞን -2፣ በጎህ ሪል ኤስቴት ወደ ፋኑኤል ቤተክርስቲያን፤ የኤሌክትሪክ ኃይል ይቋረጣል፡፡
በመሆኑም ከላይ በተጠቀሱት አካባቢዎች የምትገኙ ክቡራን ደንበኞች ከወዲሁ ቅድመ ዝግጅት እንድታደረጉ እያሳወቅን፤ የጥገናው ሥራ ተጠናቆ የኃይል አቅርቦቱ እስኪመለስ በትግዕስት እንድትጠብቁን በአክብሮት እንገልፃለን፡፡
#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት
✅ከጠዋቱ 2:00 እስከ 9:00
👉በለገጣፎ፣ በሲዲሲ፣ በኮሰሮ፣ በኤሞሌስ ፋብሪካ፣ በካሰዴ፣ በጣፎ፣ በ44 ማዞሪያ ፣ በሰንዳፋ ጫፍ፤
✅ከጠዋቱ 2:30 እስከ 9:30
👉በወሰን ግሮሰሪ፣ በሲኤምሲ ሚካኤል፣ በካራሎ፣ በየካ አባዶ የጋራ መኖሪያ ቤቶች፣ በሸገር ዳቦ፣ በወይብላ ማርያም፣
👉በአውጉስታ፣ በአንፎ፣ በወይራ ሰፈር፣ በወይራ የጋራ መኖሪያ ቤቶች፣ በሞቢል ፣ በራሺያ ካምፕ፣ በተዘንአ ሆስፒታል ፣ በሙስና ሰፈር፣ በኮፊ ሲቲ አካባቢ፣ በኢነዲያና ት/ቤት አካባቢ፤
✅ከረፋዱ 3:00 እስከ 9:30
👉በማርቆስ መጋዘን ፣ በቀጨኔ 8 ቁጥር ማዞሪያ፣ በቀጨኔ 1ኛ፣ 2ኛ እና 3ኛ መንገድ ፣ በይመር ውሃ ፣ በመቀጠያ፣ በ19 ታቦት ማደሪያ፣ በመታፈሪ ሰፈር፣ በጴጥሮስ ሆስፒታል፣ በሽሮ ሜዳ፤
✅ከረፋዱ 3:00 እስከ ምሽቱ 12:00
👉በጀርመን ድልድይ ፣ በፈረንሳይ ኤምባሲ ወደ ጉራራ፣ በብሎኬት ገበያ፣ በኪዩር ሆስፒታል ፣ በራሳ ካሳ ክሊኒክ፣ በአቦ ቤተክርስቲያን፣ በእንጦጦ ኪዳነ-ምሕረት ቤተክርስቲያን፤
✅ከረፋዱ 4:00 እስከ 8:00
👉በቡልቡላ ሙሉውን ፣ በሳሪስ አቦ፣ በቡልቡላ ማርያም ማዞሪያ፤
✅ከረፋዱ 4:00 እስከ 9:00
👉በመሪ ኮንዶሚኒየም ፣ በአያት ዞን -1 እና ዞን -2፣ በጎህ ሪል ኤስቴት ወደ ፋኑኤል ቤተክርስቲያን፤ የኤሌክትሪክ ኃይል ይቋረጣል፡፡
በመሆኑም ከላይ በተጠቀሱት አካባቢዎች የምትገኙ ክቡራን ደንበኞች ከወዲሁ ቅድመ ዝግጅት እንድታደረጉ እያሳወቅን፤ የጥገናው ሥራ ተጠናቆ የኃይል አቅርቦቱ እስኪመለስ በትግዕስት እንድትጠብቁን በአክብሮት እንገልፃለን፡፡
#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት
30 days ago
የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ ስልጣኔና የሥራ ባህል ፈተና
**********************
(የዕለቱ መልክዕት)
የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ መመረቅ ተራ የህንፃዎች ስብስብ ሳይሆን የኢትዮጵያን የከተማነት መልክዓ-ምድር በአጭር ጊዜ የመቀየር ትልቅ ማሳያ ነው። የዛሬ ሁለት ዓመት መኪና የማይደርስበት ገጠር የነበረው ይሄው ቀጠና ዛሬ በዘመናዊ አስፓልት፣ በቤት ግንባታ እና በአረንጓዴ መናፈሻዎች ደምቆ የአዲስ አበባ አዲስ የኢኮኖሚ ማዕከል ሆኗል።
ይህ ዓይነቱ መሠረተ-ልማት የውጭ ኢንቨስተሮች ችግር ሲፈጠር ጥለውት ለሚሄዱት የብድር ፓርክ ሳይሆን ነገ የሀገራችንን የኢንዱስትሪ መፃኢ እድል ለሚወስኑት የሀገር ውስጥ ወጣቶች እንደ "መዋዕለ-ህጻናት" የሚያገለግል የስትራቴጂ ለውጥ ነው፤ አባቶቻችን "የአባት እዳ ለልጅ፣ የቤት እዳ ለባለቤት" እንደሚሉት ሀገርን በራስ ልጅ እውቀትና አቅም ካልገነቡት የሰው እጅ መመልከት ማብቂያ የለውም።
ሆኖም ግን ይህንን አካላዊ ለውጥ ወደ ዘላቂ ብልጽግና ለመቀየር ትልቁ ፈተና የዜጎች የሥራ ባህልና የአስተሳሰብ አድማስ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ተናግረዋል። በሀገራችን በአንድ በኩል "ሥራ የለም" የሚል ሰበብ እየተደመጠ፣ በሌላ በኩል የሰው ኃይል እጥረት መከሰቱ ትልቅ እንቆቅልሽ ሆኗል፤፡ ይህማ "ሰነፍ እረኛ ከጅብ ይማከራል" እንደሚባለው ሆኖ ሥራን እየናቁ የሥራ እጥነትን ማማረር ነው።
ይህንን ክፍተት ለመሙላት የውጭ ሀገር ዜጎች ወደ ኢትዮጵያ እየገቡ በመሆኑ ዜጎች ከተራ ወሬና የሶሻል ሚዲያ ስድብ ወጥተው፣ "ሳይቀድሙኝ የቀደሙትን መቅደም" እንዲሉ ላባቸውን በማንጠባጠብ የሥራ እድሎችን ለመጠቀም በአስቸኳይ መንቃት አለባቸው።
"እጅ ከአፍ አይጠፋም" እንዲሉ ልማት ከድህነት መውጫ ብቸኛ መንገድ በመሆኑ አርሶ አደሩንና አቅመ-ደካሞችን ያቀፈ መሆን እንዳለበት የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ ህያው ማሳያ ነው። በሀገራችን በሚሰሩ ልማቶች አርሶ አደሩን አፈናቅሎ ከመጣል ይልቅ ምቹ የገበያ ሁኔታ መፈጠሩ፣ የጎዳና ተዳዳሪዎችንና በቡና ቤት ያሉ እህቶችን አሰልጥኖ ወደ ሥራ ማስገባት፣ ኢኮኖሚው 10.2 ፐርሰንት እንዲያድግ ከሚያደርገው የቁጥር ስሌት ባሻገር ማህበራዊ ፍትህን ያረጋገጠ ትውልድ የመገንባት ትልቅ ህልም ነው።
በመሆኑም የተጀመረው ትልቅ ጉዞ እንዳይደናቀፍ በሥራው ውስጥ የሚዘሩ "የሌብነት አረሞች" በአስቸኳይ ሊነቀሉ እንደሚገባ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጠንካራ ማስጠንቀቂያ ተሰጥቷል፡፡ ሙስና የሀገርን ልፋት የሚያቀልጥ አደገኛ ደዌ ነውና። የገንዘብም ሆነ የጊዜ እጥረት ሳይበግረው በንፁህ ልቦና እየተከናወነ ያለው ለውጥ ስኬታማ የሚሆነው ዜጎች በእምነት፣ በቋንቋ እና በጾታ ሳይገፋፉ እርስ በርስ ሲከባበሩ ብቻ ነው፤ ምክንያቱም "ድር ቢያብር አንበሳ ያስር" ነውና።
"ልጆቻችን በፍጹም አይለምኑም" የሚለውን የተስፋ ስንቅ ይዞ የኢትዮጵያን ብልጽግና በጋራ ለማየት እያንዳንዱ ዜጋ ጓዳው እስኪደርስ ሳይሆን በሰፈሩ ለሚመጣው ለውጥ አጋዥና የቀና ልብ ያለው መሆን ይጠበቅበታል።
የኢቢሲ ዶት ስትሪም ኤዲቶሪያል
**********************
(የዕለቱ መልክዕት)
የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ መመረቅ ተራ የህንፃዎች ስብስብ ሳይሆን የኢትዮጵያን የከተማነት መልክዓ-ምድር በአጭር ጊዜ የመቀየር ትልቅ ማሳያ ነው። የዛሬ ሁለት ዓመት መኪና የማይደርስበት ገጠር የነበረው ይሄው ቀጠና ዛሬ በዘመናዊ አስፓልት፣ በቤት ግንባታ እና በአረንጓዴ መናፈሻዎች ደምቆ የአዲስ አበባ አዲስ የኢኮኖሚ ማዕከል ሆኗል።
ይህ ዓይነቱ መሠረተ-ልማት የውጭ ኢንቨስተሮች ችግር ሲፈጠር ጥለውት ለሚሄዱት የብድር ፓርክ ሳይሆን ነገ የሀገራችንን የኢንዱስትሪ መፃኢ እድል ለሚወስኑት የሀገር ውስጥ ወጣቶች እንደ "መዋዕለ-ህጻናት" የሚያገለግል የስትራቴጂ ለውጥ ነው፤ አባቶቻችን "የአባት እዳ ለልጅ፣ የቤት እዳ ለባለቤት" እንደሚሉት ሀገርን በራስ ልጅ እውቀትና አቅም ካልገነቡት የሰው እጅ መመልከት ማብቂያ የለውም።
ሆኖም ግን ይህንን አካላዊ ለውጥ ወደ ዘላቂ ብልጽግና ለመቀየር ትልቁ ፈተና የዜጎች የሥራ ባህልና የአስተሳሰብ አድማስ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ተናግረዋል። በሀገራችን በአንድ በኩል "ሥራ የለም" የሚል ሰበብ እየተደመጠ፣ በሌላ በኩል የሰው ኃይል እጥረት መከሰቱ ትልቅ እንቆቅልሽ ሆኗል፤፡ ይህማ "ሰነፍ እረኛ ከጅብ ይማከራል" እንደሚባለው ሆኖ ሥራን እየናቁ የሥራ እጥነትን ማማረር ነው።
ይህንን ክፍተት ለመሙላት የውጭ ሀገር ዜጎች ወደ ኢትዮጵያ እየገቡ በመሆኑ ዜጎች ከተራ ወሬና የሶሻል ሚዲያ ስድብ ወጥተው፣ "ሳይቀድሙኝ የቀደሙትን መቅደም" እንዲሉ ላባቸውን በማንጠባጠብ የሥራ እድሎችን ለመጠቀም በአስቸኳይ መንቃት አለባቸው።
"እጅ ከአፍ አይጠፋም" እንዲሉ ልማት ከድህነት መውጫ ብቸኛ መንገድ በመሆኑ አርሶ አደሩንና አቅመ-ደካሞችን ያቀፈ መሆን እንዳለበት የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ ህያው ማሳያ ነው። በሀገራችን በሚሰሩ ልማቶች አርሶ አደሩን አፈናቅሎ ከመጣል ይልቅ ምቹ የገበያ ሁኔታ መፈጠሩ፣ የጎዳና ተዳዳሪዎችንና በቡና ቤት ያሉ እህቶችን አሰልጥኖ ወደ ሥራ ማስገባት፣ ኢኮኖሚው 10.2 ፐርሰንት እንዲያድግ ከሚያደርገው የቁጥር ስሌት ባሻገር ማህበራዊ ፍትህን ያረጋገጠ ትውልድ የመገንባት ትልቅ ህልም ነው።
በመሆኑም የተጀመረው ትልቅ ጉዞ እንዳይደናቀፍ በሥራው ውስጥ የሚዘሩ "የሌብነት አረሞች" በአስቸኳይ ሊነቀሉ እንደሚገባ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጠንካራ ማስጠንቀቂያ ተሰጥቷል፡፡ ሙስና የሀገርን ልፋት የሚያቀልጥ አደገኛ ደዌ ነውና። የገንዘብም ሆነ የጊዜ እጥረት ሳይበግረው በንፁህ ልቦና እየተከናወነ ያለው ለውጥ ስኬታማ የሚሆነው ዜጎች በእምነት፣ በቋንቋ እና በጾታ ሳይገፋፉ እርስ በርስ ሲከባበሩ ብቻ ነው፤ ምክንያቱም "ድር ቢያብር አንበሳ ያስር" ነውና።
"ልጆቻችን በፍጹም አይለምኑም" የሚለውን የተስፋ ስንቅ ይዞ የኢትዮጵያን ብልጽግና በጋራ ለማየት እያንዳንዱ ዜጋ ጓዳው እስኪደርስ ሳይሆን በሰፈሩ ለሚመጣው ለውጥ አጋዥና የቀና ልብ ያለው መሆን ይጠበቅበታል።
የኢቢሲ ዶት ስትሪም ኤዲቶሪያል
1 month ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) ለረጅም ጊዜ አዲስ አበባ በሚገኘው ማዕከላዊ መስሪያ ቤት ብቻ ሲሰጥ የቆየው እና ለበርካታ ዜጎች እንግልት ሲፈጥር የነበረው የወንጀል ነፃ ማስረጃ አሰጣጥ ሂደት ከዛሬ ግንቦት 6 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ተሻሽሎ በአካባቢ ደረጃ እንዲሰጥ መወሰኑን የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ አስታወቀ። ውሳኔው በተለይም ወደ መካከለኛው ምስራቅ አገራት ለስራ ለሚሰማሩ ዜጎች የነበረባቸውን የቢሮክራሲ ውጣ ውረድ የሚቀርፍ ትልቅ እፎይታን ይዞ መጥቷል።
ዘ-ሐበሻ የተመለከተው፣ የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ባወጣው ይፋዊ መግለጫ እንዳብራራው ማንኛውም ወደ መካከለኛው ምስራቅ አገራት ለመጓዝ የወንጀል ነፃ ሰርተፊኬት የሚፈልግ ተገልጋይ ከዛሬ ጀምሮ በአካል አዲስ አበባ ወደሚገኘው የፎረንሲክ ወንጀል ምርመራ እና አሻራ ምርመራ ዋና ክፍል መምጣት አይጠበቅበትም። ከዚህ ይልቅ አገልግሎት ፈላጊዎች በስራ እና ክህሎት ሚኒስቴር በተዘጋጁ ማዕከላት አማካኝነት በየአካባቢያቸው፣ እንዲሁም የጉዞ ሂደቱን በሚያስፈጽሙላቸው ህጋዊ ኤጀንሲዎች በኩል ማስረጃውን በቀላሉ ማግኘት ይችላሉ። ይህ አዲስ አሰራር ዜጎች ከየክልሉ ወደ ዋና ከተማው የሚያደርጉትን አላስፈላጊ ጉዞ በማስቀረት ጊዜያቸውን እና ገንዘባቸውን የሚቆጥብ ዘመናዊ አካሄድ መሆኑ ተገልጿል።
በየዓመቱ በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን የተሻለ ህይወት ፍለጋ በህጋዊ መንገድ ወደ ተለያዩ የአረብ አገራት ያቀናሉ። ይህንን ጉዞ ለማድረግ ከሚጠየቁት ዋነኛ ሰነዶች መካከል አንዱ ተጓዡ የወንጀል ሪከርድ እንደሌለበት የሚያረጋግጠው ሰርተፊኬት ሲሆን ከዚህ ቀደም ዜጎች ይህንን ሰነድ ለማግኘት ብቻ ራቅ ካሉ አካባቢዎች ወደ አዲስ አበባ በመምጣት ለቀናት ለእንግልት፣ ለሙስና እና ለከፍተኛ ወጪ ይዳረጉ እንደነበር ይታወቃል። ይህንንም በተደጋጋሚ በዘ-ሐበሻ ዜና ስንዘግብ ቆይተናል። የፌደራል ፖሊስ ይህንን የቆየ እና አሳሳቢ ክፍተት በመረዳት ከስራ እና ክህሎት ሚኒስቴር ጋር በመቀናጀት አገልግሎቱን በቴክኖሎጂ ታግዞ ተደራሽ ማድረጉ፣ መንግስት የዜጎችን ደህንነት እና ምቾት ለመጠበቅ፣ እንዲሁም ህገወጥ የሰዎች ዝውውርን በመቀነስ ህጋዊ የጉዞ መስመሩን ለማሳለጥ እያደረገ ባለው ጥረት ውስጥ እንደ አንድ ትልቅ እና ሚዛናዊ እርምጃ የሚታይ ነው። ፖሊስ አዲሱ አሰራር ዜጎችን በሰብዓዊነት ከማገልገል መርህ ጋር የተቆራኘ መሆኑንም አጽንኦት ሰጥቷል።
ዘ-ሐበሻ የተመለከተው፣ የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ባወጣው ይፋዊ መግለጫ እንዳብራራው ማንኛውም ወደ መካከለኛው ምስራቅ አገራት ለመጓዝ የወንጀል ነፃ ሰርተፊኬት የሚፈልግ ተገልጋይ ከዛሬ ጀምሮ በአካል አዲስ አበባ ወደሚገኘው የፎረንሲክ ወንጀል ምርመራ እና አሻራ ምርመራ ዋና ክፍል መምጣት አይጠበቅበትም። ከዚህ ይልቅ አገልግሎት ፈላጊዎች በስራ እና ክህሎት ሚኒስቴር በተዘጋጁ ማዕከላት አማካኝነት በየአካባቢያቸው፣ እንዲሁም የጉዞ ሂደቱን በሚያስፈጽሙላቸው ህጋዊ ኤጀንሲዎች በኩል ማስረጃውን በቀላሉ ማግኘት ይችላሉ። ይህ አዲስ አሰራር ዜጎች ከየክልሉ ወደ ዋና ከተማው የሚያደርጉትን አላስፈላጊ ጉዞ በማስቀረት ጊዜያቸውን እና ገንዘባቸውን የሚቆጥብ ዘመናዊ አካሄድ መሆኑ ተገልጿል።
በየዓመቱ በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን የተሻለ ህይወት ፍለጋ በህጋዊ መንገድ ወደ ተለያዩ የአረብ አገራት ያቀናሉ። ይህንን ጉዞ ለማድረግ ከሚጠየቁት ዋነኛ ሰነዶች መካከል አንዱ ተጓዡ የወንጀል ሪከርድ እንደሌለበት የሚያረጋግጠው ሰርተፊኬት ሲሆን ከዚህ ቀደም ዜጎች ይህንን ሰነድ ለማግኘት ብቻ ራቅ ካሉ አካባቢዎች ወደ አዲስ አበባ በመምጣት ለቀናት ለእንግልት፣ ለሙስና እና ለከፍተኛ ወጪ ይዳረጉ እንደነበር ይታወቃል። ይህንንም በተደጋጋሚ በዘ-ሐበሻ ዜና ስንዘግብ ቆይተናል። የፌደራል ፖሊስ ይህንን የቆየ እና አሳሳቢ ክፍተት በመረዳት ከስራ እና ክህሎት ሚኒስቴር ጋር በመቀናጀት አገልግሎቱን በቴክኖሎጂ ታግዞ ተደራሽ ማድረጉ፣ መንግስት የዜጎችን ደህንነት እና ምቾት ለመጠበቅ፣ እንዲሁም ህገወጥ የሰዎች ዝውውርን በመቀነስ ህጋዊ የጉዞ መስመሩን ለማሳለጥ እያደረገ ባለው ጥረት ውስጥ እንደ አንድ ትልቅ እና ሚዛናዊ እርምጃ የሚታይ ነው። ፖሊስ አዲሱ አሰራር ዜጎችን በሰብዓዊነት ከማገልገል መርህ ጋር የተቆራኘ መሆኑንም አጽንኦት ሰጥቷል።
1 month ago
1 ሺህ 139 የኤሌክትሪክ አገልግሎት ሠራተኞች በስነምግባር ጥሰት ተቀጡ
#ethiopia | የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ባለፉት ዘጠኝ ወራት የሥነ ምግባር ጉድለትና ብልሹ አሠራር በፈጸሙ 1 ሺህ 139 ሠራተኞቹ ላይ የተለያዩ አስተዳደራዊ እርምጃዎችን መውሰዱን አስታወቀ።
እርምጃ ከተወሰደባቸው መካከል 16 ሠራተኞች ከሥራ የተሰናበቱ ሲሆን 721 የሚሆኑት ደግሞ የደሞዝ ቅጣት ተጥሎባቸዋል። ቀሪዎቹ 402 ሠራተኞች የጽሑፍ ማስጠንቀቂያ ተሰጥቷቸዋል።
ከተወሰዱት እርምጃዎች ውስጥ 103ቱ ከደንበኞች በደረሱ ጥቆማዎች መሠረት የተከናወኑ ሲሆኑ ቀሪዎቹ 1 ሺህ 36 ጉዳዮች በተቋሙ የውስጥ ቁጥጥር ሥርዓት የተደረሰባቸው ናቸው።
ተቋሙ የሙስና መጠቆሚያ መተግበሪያንና ሌሎች አማራጮችን በመጠቀም ከደንበኞች የደረሱትን 427 ጥቆማዎች መመርመሩን ገልጿል።
በዚህም መሠረት በደንበኞች ጥቆማ ምክንያት 7 ሠራተኞች ከሥራ የተሰናበቱ ሲሆን 80 የደሞዝ ቅጣት፣ 14 የጽሑፍ ማስጠንቀቂያና 2 ከኃላፊነት የማንሳት እርምጃዎች ተፈጽመዋል።
አገልግሎቱ የብልሹ አሠራር ጥቆማዎች ከሚቀርቡባቸው ዋና ዋና ጉዳዮች መካከል የአዲስ ቆጣሪ ጥያቄ፣ የኃይል መቆራረጥ፣ የጥገና መዘግየት፣ የቆጣሪ ንባብና የቢል አሰባሰብ እንዲሁም የንብረት አያያዝ እንደሚገኙበት ጠቅሷል።
ደንበኞች በድረ ገጽ (www.eeuethics.et) አማካኝነት ጥቆማዎችን እንዲሰጡ ያበረታታው ተቋሙ፣ ለጠቋሚዎች አስፈላጊውን ጥበቃና እውቅና እንደሚሰጥም አረጋግጧል።
ይህም አሠራር ተቋሙ ብልሹ አሠራሮችን ለመታገል ያለውን ቁርጠኝነት የሚያሳይ መሆኑ ተገልጿል።
#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት #ሙስና #አስተዳደራዊእርምጃ #መልካምአስተዳደር #ኢትዮጵያ #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ባለፉት ዘጠኝ ወራት የሥነ ምግባር ጉድለትና ብልሹ አሠራር በፈጸሙ 1 ሺህ 139 ሠራተኞቹ ላይ የተለያዩ አስተዳደራዊ እርምጃዎችን መውሰዱን አስታወቀ።
እርምጃ ከተወሰደባቸው መካከል 16 ሠራተኞች ከሥራ የተሰናበቱ ሲሆን 721 የሚሆኑት ደግሞ የደሞዝ ቅጣት ተጥሎባቸዋል። ቀሪዎቹ 402 ሠራተኞች የጽሑፍ ማስጠንቀቂያ ተሰጥቷቸዋል።
ከተወሰዱት እርምጃዎች ውስጥ 103ቱ ከደንበኞች በደረሱ ጥቆማዎች መሠረት የተከናወኑ ሲሆኑ ቀሪዎቹ 1 ሺህ 36 ጉዳዮች በተቋሙ የውስጥ ቁጥጥር ሥርዓት የተደረሰባቸው ናቸው።
ተቋሙ የሙስና መጠቆሚያ መተግበሪያንና ሌሎች አማራጮችን በመጠቀም ከደንበኞች የደረሱትን 427 ጥቆማዎች መመርመሩን ገልጿል።
በዚህም መሠረት በደንበኞች ጥቆማ ምክንያት 7 ሠራተኞች ከሥራ የተሰናበቱ ሲሆን 80 የደሞዝ ቅጣት፣ 14 የጽሑፍ ማስጠንቀቂያና 2 ከኃላፊነት የማንሳት እርምጃዎች ተፈጽመዋል።
አገልግሎቱ የብልሹ አሠራር ጥቆማዎች ከሚቀርቡባቸው ዋና ዋና ጉዳዮች መካከል የአዲስ ቆጣሪ ጥያቄ፣ የኃይል መቆራረጥ፣ የጥገና መዘግየት፣ የቆጣሪ ንባብና የቢል አሰባሰብ እንዲሁም የንብረት አያያዝ እንደሚገኙበት ጠቅሷል።
ደንበኞች በድረ ገጽ (www.eeuethics.et) አማካኝነት ጥቆማዎችን እንዲሰጡ ያበረታታው ተቋሙ፣ ለጠቋሚዎች አስፈላጊውን ጥበቃና እውቅና እንደሚሰጥም አረጋግጧል።
ይህም አሠራር ተቋሙ ብልሹ አሠራሮችን ለመታገል ያለውን ቁርጠኝነት የሚያሳይ መሆኑ ተገልጿል።
#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት #ሙስና #አስተዳደራዊእርምጃ #መልካምአስተዳደር #ኢትዮጵያ #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
Sponsored by
Surafel
1 month ago
ወ/ሮ በረከት ወርቁ (በረከት ገበሬዋ)ን ጨምሮ 4 ሰዎችን በወንጀል እንደሚፈልጋቸው የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ አስታወቀ።
ፖሊስ በከባድ የሙስና ወንጀል እንደሚፈልጋቸው ነው ያስታወቀው።
ግለሰቦቹ፥ የኢትዮጵያ ነዳጅና ኢነርጂ ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተርና የኢትዮጵያ ነዳጅ አቅራቢ ድርጅት ዋና ዳይሬክተርን ጨምሮ በገበያ ላይ የነዳጅ እጥረት እንዲከሰት አድርገዋል ተብለው ክስ ከተመሰረተባቸው 13 ግለሰቦች መካከል ናቸው።
seledadotio
seledadotio
ፖሊስ በከባድ የሙስና ወንጀል እንደሚፈልጋቸው ነው ያስታወቀው።
ግለሰቦቹ፥ የኢትዮጵያ ነዳጅና ኢነርጂ ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተርና የኢትዮጵያ ነዳጅ አቅራቢ ድርጅት ዋና ዳይሬክተርን ጨምሮ በገበያ ላይ የነዳጅ እጥረት እንዲከሰት አድርገዋል ተብለው ክስ ከተመሰረተባቸው 13 ግለሰቦች መካከል ናቸው።
seledadotio
seledadotio
1 month ago
በፖሊስ የምትፈለገው በረከት ወርቁ በሰጠችው ምላሽ በባለስልጣናት ላይ ክስ ሰነዘረች
በኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ በከባድ የሙስና ወንጀል ከሚፈለጉ አራት ግለሰቦች መካከል አንዷ የሆነችው በረከት ወርቁ በይፋዊ የማህበራዊ ትስስር ገጿ ባስተላለፈችው መልዕክት የቀረበባትን ክስ አስተባበለች።
በረከት ወርቁ በሰጠችው ምላሽ "ምንም በማላውቀው ጉዳይ በወንጀል ተፈላጊ ሆንኩ" ስትል የገለጸች ሲሆን ፖሊስ ስምንት ሚሊዮን ብር ሀገር አሳጥተሻል በሚል ያቀረበው ክስ መሠረተ ቢስ መሆኑን ተከራክራለች።
ይልቁንም እናንተ የወሰዳችሁብኝ ከ15 ሚሊዮን ብር በላይ ነው ስትል በባለስልጣናት ላይ የመልስ ክስ ሰንዝራለች።
በተጨማሪም አብሯት በዝርዝሩ ውስጥ ስለተጠቀሰው አቶ አቡሽ አየለ ስትገልጽ ግለሰቡ ለብሔራዊ ባንክ በኩንታል ወርቅ የሚያስገቡና 28 የወርቅ ማውጫ ያላቸው ትልቅ ነጋዴ መሆናቸውን ጠቅሳለች።
በወርቅና ነዳጅ ላይ የሚሳተፉ ጥቂት ቡድኖች ሌሎቻችን እንድንወገድ ፈርደውብናል ስትል የጉዳዩ መነሻ የጥቅም ግጭት እንደሆነ አመልክታለች።
በረከት ወርቁ በጋምቤላ ክልል ኢታንግ ልዩ ወረዳ በወርቅ ማዕድን ልማት ዘርፍ ለመሰማራት የሚያስችል የኢንቨስትመንት ሰርተፊኬት እንዳላት ባያያዘችው ሰነድ ገልፃለች
በኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ በከባድ የሙስና ወንጀል ከሚፈለጉ አራት ግለሰቦች መካከል አንዷ የሆነችው በረከት ወርቁ በይፋዊ የማህበራዊ ትስስር ገጿ ባስተላለፈችው መልዕክት የቀረበባትን ክስ አስተባበለች።
በረከት ወርቁ በሰጠችው ምላሽ "ምንም በማላውቀው ጉዳይ በወንጀል ተፈላጊ ሆንኩ" ስትል የገለጸች ሲሆን ፖሊስ ስምንት ሚሊዮን ብር ሀገር አሳጥተሻል በሚል ያቀረበው ክስ መሠረተ ቢስ መሆኑን ተከራክራለች።
ይልቁንም እናንተ የወሰዳችሁብኝ ከ15 ሚሊዮን ብር በላይ ነው ስትል በባለስልጣናት ላይ የመልስ ክስ ሰንዝራለች።
በተጨማሪም አብሯት በዝርዝሩ ውስጥ ስለተጠቀሰው አቶ አቡሽ አየለ ስትገልጽ ግለሰቡ ለብሔራዊ ባንክ በኩንታል ወርቅ የሚያስገቡና 28 የወርቅ ማውጫ ያላቸው ትልቅ ነጋዴ መሆናቸውን ጠቅሳለች።
በወርቅና ነዳጅ ላይ የሚሳተፉ ጥቂት ቡድኖች ሌሎቻችን እንድንወገድ ፈርደውብናል ስትል የጉዳዩ መነሻ የጥቅም ግጭት እንደሆነ አመልክታለች።
በረከት ወርቁ በጋምቤላ ክልል ኢታንግ ልዩ ወረዳ በወርቅ ማዕድን ልማት ዘርፍ ለመሰማራት የሚያስችል የኢንቨስትመንት ሰርተፊኬት እንዳላት ባያያዘችው ሰነድ ገልፃለች
Comments