9 days ago
ቀኝ አዝማች በኩረ ምዕመናን ትዛዙ ኮሬ የኢትዮጵያን ባህል፣ ቱሪዝምና በጎ አድራጎት በማስፋፋት የሚታወቁ ታዋቂ ኢንተርፕረነር፣ የባህል አምባሳደር እና ሀገር በቀል ሽማግሌ ናቸው። በተለይም በኢትዮጵያ የመጀመሪያዎቹን እና ግዙፍ የባህል ምግብ ቤቶች አንዱ የሆነውን ዮድ አቢሲኒያ (Yod Abyssinia) ባህላዊ ምግብ ቤት በመመስረታቸው በሰፊው ይታወቃሉ።
ስለ ቀኝ አዝማች ትዛዙ ኮሬ ዋና ዋና መረጃዎች
የዮድ አቢሲኒያ መስራችና ባለቤት በ1996 ዓ.ም.
(እ.ኤ.አ. በ2003) ዮድ አቢሲኒያ ባህላዊ ምግብ ቤትን መስርተዋል።
ምግብ ቤቱ የኢትዮጵያን ብሔር ብሔረሰቦች ባህላዊ ምግቦች፣ ሙዚቃዎች እና ውዝዋዜዎች ለአገር ውስጥና ለውጭ አገር ዜጎች በማስተዋወቅ ረገድ ትልቅ ሚና አለው።
እንደ የካናዳው ጠቅላይ ሚኒስትር ጀስቲን ትሩዶ ያሉ በርካታ የዓለም መሪዎችን እና የውጭ አገር ዲፕሎማቶችን በምግብ ቤታቸው አስተናግደዋል።
❸ማኅበራዊ አገልግሎትና የበጎ አድራጎት ሥራዎች
ማኅበራዊ አገልግሎትና የበጎ አድራጎት ሥራዎች
ለተለያዩ የሃይማኖት ተቋማት እና ችግረኛ ወገኖች ከፍተኛ ድጋፍ በማድረግ ይታወቃሉ።
በበጎ አድራጎት ሥራዎቻቸው ምክንያት በ2016 ዓ.ም የፊላንትሮፒ (የበጎ አድራጎት) ሽልማት አሸናፊ ሆነዋል።
በማኅበረሰቡ ውስጥ ሰላምን ለማስፈንና እርቅ ለማውረድ እንደ ትልቅ የሀገር ሽማግሌ ሆነው ያገለግላሉ።
በጎ ተግባራት እና ማህበራዊ ሀላፊነት በመወጣት አርዓያነት ያለዉን ተግባራት በመስራት ይታወቃል።
የዓመቱን 360 ቀናት ለኢትዮጵያ ሀገራቸዉ እንዲሁም 4 ቀናት ለበጎ አድራጎት ተግባራት ሲውል ፤ 365 ኛውን ቀን ደግሞ ዕድገት እንደሚያስተዋዉቅ የሚያምኑት የድርጅቱ መስራችና የቦርድ ሰብሳቢ ቀኝ አዝማች ትዛዙ ኮሬ ናቸዉ።
የዮድ አቢሲኒያ መስራችና የቦርድ ሰብሳቢ ቀኝ አዝማች ትዛዙ ኮሬ እንዲሁም ድርጅታቸዉ 'ዮድ አቢሲኒያ'ለመቄዶንያ የአረጋውያንና የአዕምሮ ህሙማን መርጃ ማህበር፣ ለሜሪጆይ ኢትዮጵያ ፣ ለቶራ የህፃናት ማሳደጊያ ፣ ለሰሊሆም የአእምሮ ህሙማን መርጃ ፣ ለየወደቁትን እናንሳ የአረጋውያን መርጃ ማህበር ለሌሎችም በማገዝና በመርዳት ማህበራዊ ኃላፊነትን በመወጣት በጎ ስምና አርዓያነትን በተግባር ለማሳየት ችሏል።ወደፊትም ይበልጥ ተጠናክሮ ይቀጥላል።
❹እዉቅናና ሽልማት
➢የዓመቱ በጎ ሰዉ ሽልማትና እዉቅና
ጳጉሜ 3 ቀን 2016 ዓ.ም ለ12ኛ ጊዜ በተካሄደዉ የዓመቱ በጎ ሰዉ ሽልማትና እዉቅና በቅርስ ባህል እና ቱሪዝም ዘርፍ ዮድ አቢሲኒያ፡የባሕል ምግብ አዳራሽ ተሸልሟል።
የኢትዮጵያን ባህላዊ ምግቦችን ፤ ውዝዋዜዎችን እና ባህላዊ እሴቶችን ለቱሪስቶች እና ማህበረሰቡ የሚያቀርብ ተቋም ሲሆን የኢትዮጵያን እሴቶችን በማስተዋወቅ ረገድ ያስቀመጠው ደማቅ አሻራ ከፍ ያለ ነዉ።
ዮድ አቢሲኒያ ባህል ባንድ
ለቱሪስቶች የአገራችንን ብሔር ብሔረሰቦች ሙዚቃዎች ዉዝዋዜን በማሳየት ቱባ ባህላችንን ሳይበረዝና ሳይከለስ ያሳያል።
➢ የቱሪዝም አዋርድ
የአዲስ አበባ ባህል፣ ኪነ-ጥበብና ቱሪዝም ቢሮ ሐምሌ 6/2016ዓ.ም በአድዋ መታሰብያ ሙዚየም ባካሄደው የኪነ-ጥበብና ቱሪዝም ትራንስፎርሜሽን ምክር ቤት ምስረታና 1ኛ መደበኛ ጉባኤ ለከተማችን የቱሪዝም ልማትና እድገት የላቀ አስተዋጽኦ ላደረጉ የቱሪዝም ተቋማትና አካላት የቱሪዝም አዋርድ ከተሰጡት መካከል አንዱ ዮድ አቢሲኒያ የባህል ምግብ አዳራሽ ነዉ።
የቱሪዝም ተቋማቱ በሚሰጡት የአገልግሎት ጥራት ባላቸው የቱሪዝም ፈጠራ ስራ እንዲሁም የቱሪስት አያያዝና የመሳሰሉት መስፈርቶችን መነሻ በማድረግ ከዘርፉ 1ኛ በመዉጣት ዮድ አቢሲኒያ የባህል ምግብ አዳራሽ፣የቱሪዝም አዋርድ ተሸልሟል።
➢"የ8ኛዉ የአርአያ ሰው ሽልማት"
ተቀማጭነቱን በሀገረ አሜሪካ ዳላስ ቴክሳስ ያደረገው ዓድዋ የባህልና የታሪክ ኅብረት ለትርፍ ያልተቋቋመ ግብረ ሰናይ ድርጅት ሲሆን በዋናነትም ለኢትዮጵያና ለኢትዮጵያውያን አርአያ የሚሆን ሥራ ለሚሠሩ ግለሰቦችና ተቋማት"የአርአያ ሰው ሽልማት" በሚል ዕውቅና ይሰጣል፡፡
ለ8ኛ ግዜ በአዲስ አበባ ዮድ አቢሲኒያ የባህል አዳራሽ ሰኔ 13 ቀን 2016 ዓ.ም በተመሳሳይ መልኩ ለሀገር ባለውለታዎች በተለይም በባህል ልማት፣ በተፈጥሮ ጥበቃ፣ በቱሪዝም እና ቅርስ እንዲሁም በታሪክ መስኮች ለሀገራቸው አስተዋጽኦ ላበረከቱ ግለሰቦችና ተቋማት ሽልማት ከተሰጣቸው መካከል ዮድ አቢሲኒያ የባህል ምግብ አዳራሽ አንዱ ነዉ።
ዓለም አቀፍ እውቅና
የኢትዮጵያን ባህልና ቱሪዝም በዓለም አቀፍ ደረጃ በማስተዋወቃቸው “የባህልና ቱሪዝም አምባሳደር” የሚል ክብር ተሰጥቷቸዋል።
በቅርቡ (እ.ኤ.አ በ2025) በአሜሪካ ሲያትል በተካሄደው የ42ኛው የኢትዮጵያውያን የስፖርትና ባህል ፌስቲቫል (ESFNA) ላይ ለሀገራቸው ላበረከቱት የላቀ አስተዋፅኦ ልዩ የክብር ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።
❺ዋና ዋና ቅርንጫፎችና አድራሻዎች
ዮድ አቢሲኒያ በአዲስ አበባ በተለያዩ ቁልፍ ቦታዎች ቅርንጫፎችን ከፍቶ ይገኛል፦
ቦሌ ቅርንጫፍ (ዋናው)፦ ቦሌ መድኃኔዓለም አካባቢ፣ ከብራስ ሆስፒታል ከፍ ብሎ የሚገኝ የነበረ ሲሆን አሁን ቀድሞ ከነበረበት በ100 ሜትር ገባ ብሎ ኬኬር ህንፃ አጠገብ ይገኛል።ለቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ቅርብ በመሆኑ ለቱሪስቶች ተመራጭ ነው።
ፒያሳ (ቴዎድሮስ አደባባይ) ቅርንጫፍ፦ በቅርቡ በዲል ፕላዛ ፊት ለፊት የተከፈተ አዲስና ዘመናዊ የባህል አዳራሽ፣ የስፖርት ባር (Sport Bar) እና የባዛር ማዕከል ነው።
ዮድ አቢሲኒያ ኢንተርናሽናል ሆቴል፦ ሰዓሊተ ምህረት አደባባይ ከፍ ብሎ፣ ወደ ወሰን በሚወስደው መንገድ ማዕድን ሚኒስቴር አጠገብ የሚገኝ ዘመናዊ ሆቴል ነው።
❻የ"ዮድ" መሪ ቃል በተግባር
የድርጅቱ መሪ ቃል የሃገራችን ኢትዮጵያን ”ባህል ፤ ታሪክ ፤ ቅርሶች እንጠብቅ፤ እናክብር ፤ ቋንቋችንን እናሳድግ ” የሚል ነው ባለፉት 22 ዓመታት የኢትዮጵያን ባህልና መስተንግዶን ጨምሮ ሲያስተዋውቅ ኖሯል ፡፡ ለዚህም አስተዋፅኦው ”የኢትዮጵያ የባህልና የቱሪዝም አምባሳደር” የሚል ዕውቅና ከመንግስት ተሰጥቶታል ፡፡
“ባህል ፤ ታሪክ ፤ ቅርሶች እንጠብቅ፤ እናክብር ፤ ቋንቋችንን እናሳድግ” በሚል መርህ ከመላው ዓለም ወደ ሃገራችን ለመጡ እንግዶች የባህል ምግብና መጠጦች መስተንግዶ በመስጠት ፣ የብሔር ብሄረሰቦችን ሙዚቃዎችና ውዝዋዜዎች በማቅረብ ፣ የሀገራችንን የታሪክ የባህልና የቱሪዝም ሃብቶችና ቅርሶቻችንን በማስተዋወቅ የኢትዮጵያን መልካም ገፅታ በመገንባት ብዙ በመስራት ”የኢትዮጵያ የባህል እና የቱሪዝም አምባሳደር” የሚል እውቅናን ለማግኘት ችሏል፡፡
"ዮድ"
ዮድ ብሂል የማነ እግዚአብሔር ገብረት ኃይለ
በእግዚአብሔር ቀኝ ያለ እሱ ኃያልና
ጽኑዕ የሆነ ነው ማለት በሌላ መልኩ"ዮድ" ማለት በጉራጌ ቋንቋ "መመስከር ወይም መናገር" ማለት ነዉ።
ከ1996ዓ.ምማለትምላለፉት 22 ዓመታት በተለያዩ ወቅቶች ወደ ሀገራችን የመጡ በርካታ የሀገራት መሪዎችን ፣ ዲፕሎማቶችን ፣ የዓለም ታላላቅ ሰዎችን፣ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት ፣ ታዋቂ ሰዎች ፣ ባለሀብቶች ፣ አትሌቶች ፣ አርቲስቶች የሚዲያ ባለሙያዎች እንዲሁም ሌሎችም በሺዎች የሚቆጠሩ ቱሪስቶችንና ኢትዮጵያዊያን እንግዶችን ተቀብሎ በፍቅርና በአክብሮት ሲያስተናግድ የቆየው ዮድ አቢሲኒያ በቀጣይም በሀገራችን ለሚከናወኑ ታላላቅ ሁነቶች ሙሉ አገልግሎት ለመስጠት ከወትሮው በተለዬ አኳኋን መዘጋጀቱ ተስተዉሏል።በ500 ብር ካፒታል እና በአነስተኛ የስራ ጅምር በጥረት የተገነባ ካምፓኒ በበርካታ ፈተናዎች ዉስጥ አልፎ ዛሬ በርካታ ቁጥር ላላቸዉ ወገኖቻችን የስራ ዕድል መፍጠር የቻለ ግዙፍ ኩባንያ ለመሆን በቅቷል።
"የሃገራችን ኢትዮጵያን ባህል ፤ ታሪክ ፤ ቅርሶች እንጠብቅ፤ እናክብር ፤ ቋንቋችንን እናሳድግ ”ዮድ አቢሲኒያ የባህል ምግብ አዳራሽ
ዘጋቢ ጋዜጠኛ ሲሳይ መንግስቴ
ስለ ቀኝ አዝማች ትዛዙ ኮሬ ዋና ዋና መረጃዎች
የዮድ አቢሲኒያ መስራችና ባለቤት በ1996 ዓ.ም.
(እ.ኤ.አ. በ2003) ዮድ አቢሲኒያ ባህላዊ ምግብ ቤትን መስርተዋል።
ምግብ ቤቱ የኢትዮጵያን ብሔር ብሔረሰቦች ባህላዊ ምግቦች፣ ሙዚቃዎች እና ውዝዋዜዎች ለአገር ውስጥና ለውጭ አገር ዜጎች በማስተዋወቅ ረገድ ትልቅ ሚና አለው።
እንደ የካናዳው ጠቅላይ ሚኒስትር ጀስቲን ትሩዶ ያሉ በርካታ የዓለም መሪዎችን እና የውጭ አገር ዲፕሎማቶችን በምግብ ቤታቸው አስተናግደዋል።
❸ማኅበራዊ አገልግሎትና የበጎ አድራጎት ሥራዎች
ማኅበራዊ አገልግሎትና የበጎ አድራጎት ሥራዎች
ለተለያዩ የሃይማኖት ተቋማት እና ችግረኛ ወገኖች ከፍተኛ ድጋፍ በማድረግ ይታወቃሉ።
በበጎ አድራጎት ሥራዎቻቸው ምክንያት በ2016 ዓ.ም የፊላንትሮፒ (የበጎ አድራጎት) ሽልማት አሸናፊ ሆነዋል።
በማኅበረሰቡ ውስጥ ሰላምን ለማስፈንና እርቅ ለማውረድ እንደ ትልቅ የሀገር ሽማግሌ ሆነው ያገለግላሉ።
በጎ ተግባራት እና ማህበራዊ ሀላፊነት በመወጣት አርዓያነት ያለዉን ተግባራት በመስራት ይታወቃል።
የዓመቱን 360 ቀናት ለኢትዮጵያ ሀገራቸዉ እንዲሁም 4 ቀናት ለበጎ አድራጎት ተግባራት ሲውል ፤ 365 ኛውን ቀን ደግሞ ዕድገት እንደሚያስተዋዉቅ የሚያምኑት የድርጅቱ መስራችና የቦርድ ሰብሳቢ ቀኝ አዝማች ትዛዙ ኮሬ ናቸዉ።
የዮድ አቢሲኒያ መስራችና የቦርድ ሰብሳቢ ቀኝ አዝማች ትዛዙ ኮሬ እንዲሁም ድርጅታቸዉ 'ዮድ አቢሲኒያ'ለመቄዶንያ የአረጋውያንና የአዕምሮ ህሙማን መርጃ ማህበር፣ ለሜሪጆይ ኢትዮጵያ ፣ ለቶራ የህፃናት ማሳደጊያ ፣ ለሰሊሆም የአእምሮ ህሙማን መርጃ ፣ ለየወደቁትን እናንሳ የአረጋውያን መርጃ ማህበር ለሌሎችም በማገዝና በመርዳት ማህበራዊ ኃላፊነትን በመወጣት በጎ ስምና አርዓያነትን በተግባር ለማሳየት ችሏል።ወደፊትም ይበልጥ ተጠናክሮ ይቀጥላል።
❹እዉቅናና ሽልማት
➢የዓመቱ በጎ ሰዉ ሽልማትና እዉቅና
ጳጉሜ 3 ቀን 2016 ዓ.ም ለ12ኛ ጊዜ በተካሄደዉ የዓመቱ በጎ ሰዉ ሽልማትና እዉቅና በቅርስ ባህል እና ቱሪዝም ዘርፍ ዮድ አቢሲኒያ፡የባሕል ምግብ አዳራሽ ተሸልሟል።
የኢትዮጵያን ባህላዊ ምግቦችን ፤ ውዝዋዜዎችን እና ባህላዊ እሴቶችን ለቱሪስቶች እና ማህበረሰቡ የሚያቀርብ ተቋም ሲሆን የኢትዮጵያን እሴቶችን በማስተዋወቅ ረገድ ያስቀመጠው ደማቅ አሻራ ከፍ ያለ ነዉ።
ዮድ አቢሲኒያ ባህል ባንድ
ለቱሪስቶች የአገራችንን ብሔር ብሔረሰቦች ሙዚቃዎች ዉዝዋዜን በማሳየት ቱባ ባህላችንን ሳይበረዝና ሳይከለስ ያሳያል።
➢ የቱሪዝም አዋርድ
የአዲስ አበባ ባህል፣ ኪነ-ጥበብና ቱሪዝም ቢሮ ሐምሌ 6/2016ዓ.ም በአድዋ መታሰብያ ሙዚየም ባካሄደው የኪነ-ጥበብና ቱሪዝም ትራንስፎርሜሽን ምክር ቤት ምስረታና 1ኛ መደበኛ ጉባኤ ለከተማችን የቱሪዝም ልማትና እድገት የላቀ አስተዋጽኦ ላደረጉ የቱሪዝም ተቋማትና አካላት የቱሪዝም አዋርድ ከተሰጡት መካከል አንዱ ዮድ አቢሲኒያ የባህል ምግብ አዳራሽ ነዉ።
የቱሪዝም ተቋማቱ በሚሰጡት የአገልግሎት ጥራት ባላቸው የቱሪዝም ፈጠራ ስራ እንዲሁም የቱሪስት አያያዝና የመሳሰሉት መስፈርቶችን መነሻ በማድረግ ከዘርፉ 1ኛ በመዉጣት ዮድ አቢሲኒያ የባህል ምግብ አዳራሽ፣የቱሪዝም አዋርድ ተሸልሟል።
➢"የ8ኛዉ የአርአያ ሰው ሽልማት"
ተቀማጭነቱን በሀገረ አሜሪካ ዳላስ ቴክሳስ ያደረገው ዓድዋ የባህልና የታሪክ ኅብረት ለትርፍ ያልተቋቋመ ግብረ ሰናይ ድርጅት ሲሆን በዋናነትም ለኢትዮጵያና ለኢትዮጵያውያን አርአያ የሚሆን ሥራ ለሚሠሩ ግለሰቦችና ተቋማት"የአርአያ ሰው ሽልማት" በሚል ዕውቅና ይሰጣል፡፡
ለ8ኛ ግዜ በአዲስ አበባ ዮድ አቢሲኒያ የባህል አዳራሽ ሰኔ 13 ቀን 2016 ዓ.ም በተመሳሳይ መልኩ ለሀገር ባለውለታዎች በተለይም በባህል ልማት፣ በተፈጥሮ ጥበቃ፣ በቱሪዝም እና ቅርስ እንዲሁም በታሪክ መስኮች ለሀገራቸው አስተዋጽኦ ላበረከቱ ግለሰቦችና ተቋማት ሽልማት ከተሰጣቸው መካከል ዮድ አቢሲኒያ የባህል ምግብ አዳራሽ አንዱ ነዉ።
ዓለም አቀፍ እውቅና
የኢትዮጵያን ባህልና ቱሪዝም በዓለም አቀፍ ደረጃ በማስተዋወቃቸው “የባህልና ቱሪዝም አምባሳደር” የሚል ክብር ተሰጥቷቸዋል።
በቅርቡ (እ.ኤ.አ በ2025) በአሜሪካ ሲያትል በተካሄደው የ42ኛው የኢትዮጵያውያን የስፖርትና ባህል ፌስቲቫል (ESFNA) ላይ ለሀገራቸው ላበረከቱት የላቀ አስተዋፅኦ ልዩ የክብር ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።
❺ዋና ዋና ቅርንጫፎችና አድራሻዎች
ዮድ አቢሲኒያ በአዲስ አበባ በተለያዩ ቁልፍ ቦታዎች ቅርንጫፎችን ከፍቶ ይገኛል፦
ቦሌ ቅርንጫፍ (ዋናው)፦ ቦሌ መድኃኔዓለም አካባቢ፣ ከብራስ ሆስፒታል ከፍ ብሎ የሚገኝ የነበረ ሲሆን አሁን ቀድሞ ከነበረበት በ100 ሜትር ገባ ብሎ ኬኬር ህንፃ አጠገብ ይገኛል።ለቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ቅርብ በመሆኑ ለቱሪስቶች ተመራጭ ነው።
ፒያሳ (ቴዎድሮስ አደባባይ) ቅርንጫፍ፦ በቅርቡ በዲል ፕላዛ ፊት ለፊት የተከፈተ አዲስና ዘመናዊ የባህል አዳራሽ፣ የስፖርት ባር (Sport Bar) እና የባዛር ማዕከል ነው።
ዮድ አቢሲኒያ ኢንተርናሽናል ሆቴል፦ ሰዓሊተ ምህረት አደባባይ ከፍ ብሎ፣ ወደ ወሰን በሚወስደው መንገድ ማዕድን ሚኒስቴር አጠገብ የሚገኝ ዘመናዊ ሆቴል ነው።
❻የ"ዮድ" መሪ ቃል በተግባር
የድርጅቱ መሪ ቃል የሃገራችን ኢትዮጵያን ”ባህል ፤ ታሪክ ፤ ቅርሶች እንጠብቅ፤ እናክብር ፤ ቋንቋችንን እናሳድግ ” የሚል ነው ባለፉት 22 ዓመታት የኢትዮጵያን ባህልና መስተንግዶን ጨምሮ ሲያስተዋውቅ ኖሯል ፡፡ ለዚህም አስተዋፅኦው ”የኢትዮጵያ የባህልና የቱሪዝም አምባሳደር” የሚል ዕውቅና ከመንግስት ተሰጥቶታል ፡፡
“ባህል ፤ ታሪክ ፤ ቅርሶች እንጠብቅ፤ እናክብር ፤ ቋንቋችንን እናሳድግ” በሚል መርህ ከመላው ዓለም ወደ ሃገራችን ለመጡ እንግዶች የባህል ምግብና መጠጦች መስተንግዶ በመስጠት ፣ የብሔር ብሄረሰቦችን ሙዚቃዎችና ውዝዋዜዎች በማቅረብ ፣ የሀገራችንን የታሪክ የባህልና የቱሪዝም ሃብቶችና ቅርሶቻችንን በማስተዋወቅ የኢትዮጵያን መልካም ገፅታ በመገንባት ብዙ በመስራት ”የኢትዮጵያ የባህል እና የቱሪዝም አምባሳደር” የሚል እውቅናን ለማግኘት ችሏል፡፡
"ዮድ"
ዮድ ብሂል የማነ እግዚአብሔር ገብረት ኃይለ
በእግዚአብሔር ቀኝ ያለ እሱ ኃያልና
ጽኑዕ የሆነ ነው ማለት በሌላ መልኩ"ዮድ" ማለት በጉራጌ ቋንቋ "መመስከር ወይም መናገር" ማለት ነዉ።
ከ1996ዓ.ምማለትምላለፉት 22 ዓመታት በተለያዩ ወቅቶች ወደ ሀገራችን የመጡ በርካታ የሀገራት መሪዎችን ፣ ዲፕሎማቶችን ፣ የዓለም ታላላቅ ሰዎችን፣ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት ፣ ታዋቂ ሰዎች ፣ ባለሀብቶች ፣ አትሌቶች ፣ አርቲስቶች የሚዲያ ባለሙያዎች እንዲሁም ሌሎችም በሺዎች የሚቆጠሩ ቱሪስቶችንና ኢትዮጵያዊያን እንግዶችን ተቀብሎ በፍቅርና በአክብሮት ሲያስተናግድ የቆየው ዮድ አቢሲኒያ በቀጣይም በሀገራችን ለሚከናወኑ ታላላቅ ሁነቶች ሙሉ አገልግሎት ለመስጠት ከወትሮው በተለዬ አኳኋን መዘጋጀቱ ተስተዉሏል።በ500 ብር ካፒታል እና በአነስተኛ የስራ ጅምር በጥረት የተገነባ ካምፓኒ በበርካታ ፈተናዎች ዉስጥ አልፎ ዛሬ በርካታ ቁጥር ላላቸዉ ወገኖቻችን የስራ ዕድል መፍጠር የቻለ ግዙፍ ኩባንያ ለመሆን በቅቷል።
"የሃገራችን ኢትዮጵያን ባህል ፤ ታሪክ ፤ ቅርሶች እንጠብቅ፤ እናክብር ፤ ቋንቋችንን እናሳድግ ”ዮድ አቢሲኒያ የባህል ምግብ አዳራሽ
ዘጋቢ ጋዜጠኛ ሲሳይ መንግስቴ
11 days ago
12 days ago
"ምስጉን ሰው" የተሰኘው መጽሐፍ በድምቀት ተመረቀ
#ethiopia | የአቶ ታምራት ተመስገንን የሕይወት እና የሥራ ታሪክ የሚተርከው "ምስጉን ሰው" የተሰኘው አዲስ መጽሐፍ ዛሬ ግንቦት 16 ቀን 2018 ዓ.ም በዲ ሊዮፖል ሆቴል በተካሄደ ስነ-ስርዓት በይፋ ተመረቀ።
ሰም እና ወርቅ ሚዲያ እና ኢንተርቴይመንት ባዘጋጀው በዚህ የመጽሐፍ የምረቃ መርሃ-ግብር ላይ የክብር እንግዶች፣ አንጋፋ የሥነ-ጽሑፍ ሰዎች፣ የባለታሪኩ ወዳጆች እና ጥሪ የተደረገላቸው በርካታ እንግዶች ታድመዋል።
መጽሐፉ በጉራጌ ዞን በእንደጋኝ ወረዳ ተወልደው በሊስትሮነትና በሌሎች እጅግ አነስተኛ የጉልበት ሥራዎች ሕይወታቸውን የጀመሩትን የአቶ ታምራት ተመስገንን የትግል ጉዞ በሰፊው ይዳስሳል።
ባለታሪኩ ይህንን ፈታኝ የሕይወት ውጣ ውረድ በፅናት አልፈው ሀገሪቱ ካሏት ታላላቅ የግንባታ ኮንትራክተሮች አንዱ ለመሆን የቻሉ ሲሆን፣ ለበርካታ ዜጎችም የሥራ ዕድል በመፍጠር በሙያቸው እንዲበቁ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከታቸው በምረቃው ላይ ተገልጿል።
አቶ ታምራት ከጠንካራ የሥራ ባህላቸው ባሻገር በማኅበረሰባዊ እና በበጎ አድራጎት ሥራዎቻቸውም በሰፊው እንደሚታወቁ በመጽሐፉ ተብራርቷል።
በችግር የተዘጉ ቤቶችን በመክፈት፣ አቅመ ደካሞችን በመደገፍ እንዲሁም ህሙማንን በማሳከም ኃላፊነታቸውን የተወጡ ምስጉን ሰው ናቸው። በተጨማሪም መንገዶችን፣ ቤተ እምነቶችን፣ የሕክምና ተቋማትን እና ትምህርት ቤቶችን በገንዘባቸውና በሙያቸው በመደገፍና በመገንባት ለአገልግሎት እንዲበቁ አድርገዋል።
ይህ የባለታሪኩን አርዓያነት ያለው ሕይወት አጉልቶ የሚያሳየው "ምስጉን ሰው" የተሰኘው መጽሐፍ፣ በሃያሲና የሥነ-ጽሑፍ መምህር ባዩልኝ አያሌው እንዲሁም በደራሲና ጋዜጠኛ ዘነበ ወላ ተጽፎ ለንባብ የበቃ ነው።
የሕይወት ታሪክ መጽሐፉ በአምስት ዋና ዋና ክፍሎች እና በአርባ ሁለት ምዕራፎች የተዋቀረ ሲሆን፣ በአጠቃላይ በሶስት መቶ ሰማንያ ሁለት ገጾች ተቀነባብሮ ቀርቧል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
#ethiopia | የአቶ ታምራት ተመስገንን የሕይወት እና የሥራ ታሪክ የሚተርከው "ምስጉን ሰው" የተሰኘው አዲስ መጽሐፍ ዛሬ ግንቦት 16 ቀን 2018 ዓ.ም በዲ ሊዮፖል ሆቴል በተካሄደ ስነ-ስርዓት በይፋ ተመረቀ።
ሰም እና ወርቅ ሚዲያ እና ኢንተርቴይመንት ባዘጋጀው በዚህ የመጽሐፍ የምረቃ መርሃ-ግብር ላይ የክብር እንግዶች፣ አንጋፋ የሥነ-ጽሑፍ ሰዎች፣ የባለታሪኩ ወዳጆች እና ጥሪ የተደረገላቸው በርካታ እንግዶች ታድመዋል።
መጽሐፉ በጉራጌ ዞን በእንደጋኝ ወረዳ ተወልደው በሊስትሮነትና በሌሎች እጅግ አነስተኛ የጉልበት ሥራዎች ሕይወታቸውን የጀመሩትን የአቶ ታምራት ተመስገንን የትግል ጉዞ በሰፊው ይዳስሳል።
ባለታሪኩ ይህንን ፈታኝ የሕይወት ውጣ ውረድ በፅናት አልፈው ሀገሪቱ ካሏት ታላላቅ የግንባታ ኮንትራክተሮች አንዱ ለመሆን የቻሉ ሲሆን፣ ለበርካታ ዜጎችም የሥራ ዕድል በመፍጠር በሙያቸው እንዲበቁ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከታቸው በምረቃው ላይ ተገልጿል።
አቶ ታምራት ከጠንካራ የሥራ ባህላቸው ባሻገር በማኅበረሰባዊ እና በበጎ አድራጎት ሥራዎቻቸውም በሰፊው እንደሚታወቁ በመጽሐፉ ተብራርቷል።
በችግር የተዘጉ ቤቶችን በመክፈት፣ አቅመ ደካሞችን በመደገፍ እንዲሁም ህሙማንን በማሳከም ኃላፊነታቸውን የተወጡ ምስጉን ሰው ናቸው። በተጨማሪም መንገዶችን፣ ቤተ እምነቶችን፣ የሕክምና ተቋማትን እና ትምህርት ቤቶችን በገንዘባቸውና በሙያቸው በመደገፍና በመገንባት ለአገልግሎት እንዲበቁ አድርገዋል።
ይህ የባለታሪኩን አርዓያነት ያለው ሕይወት አጉልቶ የሚያሳየው "ምስጉን ሰው" የተሰኘው መጽሐፍ፣ በሃያሲና የሥነ-ጽሑፍ መምህር ባዩልኝ አያሌው እንዲሁም በደራሲና ጋዜጠኛ ዘነበ ወላ ተጽፎ ለንባብ የበቃ ነው።
የሕይወት ታሪክ መጽሐፉ በአምስት ዋና ዋና ክፍሎች እና በአርባ ሁለት ምዕራፎች የተዋቀረ ሲሆን፣ በአጠቃላይ በሶስት መቶ ሰማንያ ሁለት ገጾች ተቀነባብሮ ቀርቧል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
14 days ago
በትራንስፎርመር ላይ ስርቆትና ጉዳት ያደረሱ ወንጀለኞች እስከ 13 ዓመት በሚደርስ ፅኑ እስራት ተቀጡ
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የሕዝብና የሀገር ሀብት በሆኑ የኤሌክትሪክ መሠረተ ልማቶች ላይ የሚፈጸሙ የስርቆትና የጥፋት ድርጊቶችን ለመግታት ከጸጥታ አካላትና ከኅብረተሰቡ ጋር በቅንጅት እየሠራ ይገኛል።
በዚህ ረገድ በጉራጌ ዞን ምሁር አክሊል ወረዳ በአበጅ ቀበሌ ውስጥ በሚገኝና በተቋማችን ንብረት በሆነ ትራንስፎርመር ላይ የስርቆትና ከፍተኛ የውድመት ወንጀል የፈጸሙ 5 ወጣቶች እስከ 13 ዓመት በሚደርስ ፅኑ እስራት መቀጣታቸውን የወረዳው ፖሊስ ጽህፈት ቤት አስታውቋል።
ግለሰቦቹ መጋቢት 4 ቀን 2018 ዓ.ም በትራንስፎርመሩ ላይ ያለውን የኤሌክትሪክ መስመር በመበጠስ፣ የውስጥ ገመዶችንና ብሎኖችን በመፍታት በአካባቢው የኃይል መቋረጥና በተቋሙ ንብረት ላይ ከፍተኛ ጉዳት አድርሰዋል።
ድርጊቱን ከፈጸሙ በኋላ ከአካባቢው ተሰውረው የነበሩ ቢሆንም፣ የፖሊስ አባላት ከኅብረተሰቡ በደረሳቸው ጥቆማና ባደረጉት ተከታታይ ክትትል መጋቢት 6 ቀን 2018 ዓ.ም በቁጥጥር ስር ሊያውሏቸው ችለዋል።
ፖሊስ ያጣራውን የምርመራ መዝገብ መሠረት በማድረግ የጉራጌ ዞን ፍትህ መምሪያ ባቀረበው ክስ መሠረት፣ የዞኑ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ግንቦት 13 ቀን 2018 ዓ.ም በዋለው ችሎት ወንጀለኞቹ ጥፋተኛ መሆናቸውን በማረጋገጥ ጠንከር ያለ የቅጣት ውሳኔ አስተላልፏል።
በዚህም መሠረት ተከሳሾቹ አውላቸው ክንፈ፣ ገዛኸኝ ቢኒያም፣ መላኩ ቢረዳ እና በቃሉ አለምይርጋ እያንዳንዳቸው በ13 ዓመት ፅኑ እስራት እንዲቀጡ ሲወሰን፣ አምስተኛው ተከሳሽ በረከት ጃንጊላ ደግሞ በ12 ዓመት ፅኑ እስራት እንዲቀጣ ተወስኖበታል።
የምሁር አክሊል ወረዳ መንግስት ኮምዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት የወረዳውን ፖሊስ ዋቢ በማድረግ እንደገለጸው፣ ይህ የተላለፈው ውሳኔ በሕዝብና በሀገር ሀብት ላይ መሰል የወንጀል ድርጊት ለመፈጸም በሚያስቡ አካላት ላይ ግልጽ መልእክት የሚያስተላልፍና አስተማሪ እርምጃ እንዲሆን በማሰብ መሆኑን አስታውቋል።
ተቋማችን የኤሌክትሪክ መሠረተ ልማቶችን ከጥፋት ኃይሎች ለመጠበቅ ኅብረተሰቡ እያደረገ ላለው ተሳትፎ እውቅና እየሰጠ፣ በቀጣይም መሰል አጥፊዎችን በማጋለጥ ረገድ የምታደርጉትን ጥቆማና ክትትል አጠናክራችሁ እንድትቀጥሉ ጥሪውን ያቀርባል።
#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የሕዝብና የሀገር ሀብት በሆኑ የኤሌክትሪክ መሠረተ ልማቶች ላይ የሚፈጸሙ የስርቆትና የጥፋት ድርጊቶችን ለመግታት ከጸጥታ አካላትና ከኅብረተሰቡ ጋር በቅንጅት እየሠራ ይገኛል።
በዚህ ረገድ በጉራጌ ዞን ምሁር አክሊል ወረዳ በአበጅ ቀበሌ ውስጥ በሚገኝና በተቋማችን ንብረት በሆነ ትራንስፎርመር ላይ የስርቆትና ከፍተኛ የውድመት ወንጀል የፈጸሙ 5 ወጣቶች እስከ 13 ዓመት በሚደርስ ፅኑ እስራት መቀጣታቸውን የወረዳው ፖሊስ ጽህፈት ቤት አስታውቋል።
ግለሰቦቹ መጋቢት 4 ቀን 2018 ዓ.ም በትራንስፎርመሩ ላይ ያለውን የኤሌክትሪክ መስመር በመበጠስ፣ የውስጥ ገመዶችንና ብሎኖችን በመፍታት በአካባቢው የኃይል መቋረጥና በተቋሙ ንብረት ላይ ከፍተኛ ጉዳት አድርሰዋል።
ድርጊቱን ከፈጸሙ በኋላ ከአካባቢው ተሰውረው የነበሩ ቢሆንም፣ የፖሊስ አባላት ከኅብረተሰቡ በደረሳቸው ጥቆማና ባደረጉት ተከታታይ ክትትል መጋቢት 6 ቀን 2018 ዓ.ም በቁጥጥር ስር ሊያውሏቸው ችለዋል።
ፖሊስ ያጣራውን የምርመራ መዝገብ መሠረት በማድረግ የጉራጌ ዞን ፍትህ መምሪያ ባቀረበው ክስ መሠረት፣ የዞኑ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ግንቦት 13 ቀን 2018 ዓ.ም በዋለው ችሎት ወንጀለኞቹ ጥፋተኛ መሆናቸውን በማረጋገጥ ጠንከር ያለ የቅጣት ውሳኔ አስተላልፏል።
በዚህም መሠረት ተከሳሾቹ አውላቸው ክንፈ፣ ገዛኸኝ ቢኒያም፣ መላኩ ቢረዳ እና በቃሉ አለምይርጋ እያንዳንዳቸው በ13 ዓመት ፅኑ እስራት እንዲቀጡ ሲወሰን፣ አምስተኛው ተከሳሽ በረከት ጃንጊላ ደግሞ በ12 ዓመት ፅኑ እስራት እንዲቀጣ ተወስኖበታል።
የምሁር አክሊል ወረዳ መንግስት ኮምዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት የወረዳውን ፖሊስ ዋቢ በማድረግ እንደገለጸው፣ ይህ የተላለፈው ውሳኔ በሕዝብና በሀገር ሀብት ላይ መሰል የወንጀል ድርጊት ለመፈጸም በሚያስቡ አካላት ላይ ግልጽ መልእክት የሚያስተላልፍና አስተማሪ እርምጃ እንዲሆን በማሰብ መሆኑን አስታውቋል።
ተቋማችን የኤሌክትሪክ መሠረተ ልማቶችን ከጥፋት ኃይሎች ለመጠበቅ ኅብረተሰቡ እያደረገ ላለው ተሳትፎ እውቅና እየሰጠ፣ በቀጣይም መሰል አጥፊዎችን በማጋለጥ ረገድ የምታደርጉትን ጥቆማና ክትትል አጠናክራችሁ እንድትቀጥሉ ጥሪውን ያቀርባል።
#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት
14 days ago
በነዳጅ የተበሳጨው ቻይናዊ‼️👆
ምስራቅ ጉራጌ ዞን ያሉ ለልማት የገቡ ቻይናወች በነዳጅ ምሬት ምክንያት ብዙ ኢንቨስተር እየተማረረ ነው፣ባወጣችሁት ህግ መሰረት ስሩ ይላል።
እኔ የያዝኩት ኩፖን እውነተኛ ነው የውሸት አይደለም ለምንድነው ለሌላ እየቀዳችሁ ለእኔ እምቢ የምትሉኝ ብሏል።
seledadotio
seledadotio
ምስራቅ ጉራጌ ዞን ያሉ ለልማት የገቡ ቻይናወች በነዳጅ ምሬት ምክንያት ብዙ ኢንቨስተር እየተማረረ ነው፣ባወጣችሁት ህግ መሰረት ስሩ ይላል።
እኔ የያዝኩት ኩፖን እውነተኛ ነው የውሸት አይደለም ለምንድነው ለሌላ እየቀዳችሁ ለእኔ እምቢ የምትሉኝ ብሏል።
seledadotio
seledadotio
18 days ago
“የአዶ ትዝታዎች” የተሰኘው አዲስ መጽሐፍ በፕሮፌሰር ታሪክ ወልደሚካኤል እና በአቶ ሙሉጌታ ወልደሚካኤል መጪው ቅዳሜ ግንቦት 15 ቀን 2018 ዓ.ም ይመረቃል።
መጽሐፉ፤ የአንድ ቤተሰብን ታሪክ ዋቢ በማድረግ ከጉራጌ ማህበረሰብ ምድር ተነስተው ወደ አዲስ አበባ የተደረጉ ታሪካዊና ትውልድ ተሻጋሪ የህይወት ጉዞዎችን በስፋት የሚዳስስ ነው። በተለይም ውድ አያት ኑሮን ለማሸነፍ የከፈሉትን ከፍተኛ ተጋድሎ፣ ያጋጠሟቸውን አስገራሚ ክስተቶች በሳቅና በትዝታ ታጅቦ በሚያስነብብ መልኩ እንደተከተበ ተገልጿል።
ከዚህም በተጨማሪ የክቡር አባታችን የአቶ ወልደሚካኤል አንዳግቤ እና የውድ እናታችን የወ/ሮ አስካለ ኃብተማርያም ከጉራጌ ዞን እስከ አዲስ አበባ የዘለቀውን አስደናቂ የህይወት ጉዞ፤ ህይወትን ለመለወጥና ቤተሰብን ለመገንባት ያደረጉትን ተጋድሎ፣ ያፈሩትን ሀብትና ያጋጠሟቸውን ውጣ ውረዶች በግልጽ የሚያሳይ መሆኑ ተጠቁሟል።
ይህ መጽሐፍ ፈጣሪ የሰጠንን ችሎታና ማስተዋል ለበጎ ነገር ማዋል እንደምንችል የምንማርበት፣ ከየትኛውም ከባድ ውድቀት መነሳት እንደሚቻል የሚያሳይና የትውልድ ቅብብሎሽን የሚያጸና የታሪክ መዝገብ መሆኑን የደረሰን መረጃ ያመለክታል።
የመጽሐፉ የምረቃ ሥነ-ስርዓት ቅዳሜ ግንቦት 15 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ጀምሮ ከሜክስኮ ወደ መካኒሳ በሚወስደው መንገድ፣ ከሳር ቤት አደባባይ አለፍ ብሎ በስተቀኝ በኩል በሚገኘው የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቲዎሎጂካል ሴሚናሪ (EGST) አዳራሽ በድምቀት እንደሚካሄድ ታውቋል።
በዚህ ታላቅና ታሪካዊ የምረቃ በዓል ላይ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች፣ ወዳጅ ዘመዶችና የመጽሐፍ አፍቃሪያን ተገኝተው የደስታው ተካፋይ እንዲሆኑ አዘጋጆቹ በአክብሮት ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።
መጽሐፉ፤ የአንድ ቤተሰብን ታሪክ ዋቢ በማድረግ ከጉራጌ ማህበረሰብ ምድር ተነስተው ወደ አዲስ አበባ የተደረጉ ታሪካዊና ትውልድ ተሻጋሪ የህይወት ጉዞዎችን በስፋት የሚዳስስ ነው። በተለይም ውድ አያት ኑሮን ለማሸነፍ የከፈሉትን ከፍተኛ ተጋድሎ፣ ያጋጠሟቸውን አስገራሚ ክስተቶች በሳቅና በትዝታ ታጅቦ በሚያስነብብ መልኩ እንደተከተበ ተገልጿል።
ከዚህም በተጨማሪ የክቡር አባታችን የአቶ ወልደሚካኤል አንዳግቤ እና የውድ እናታችን የወ/ሮ አስካለ ኃብተማርያም ከጉራጌ ዞን እስከ አዲስ አበባ የዘለቀውን አስደናቂ የህይወት ጉዞ፤ ህይወትን ለመለወጥና ቤተሰብን ለመገንባት ያደረጉትን ተጋድሎ፣ ያፈሩትን ሀብትና ያጋጠሟቸውን ውጣ ውረዶች በግልጽ የሚያሳይ መሆኑ ተጠቁሟል።
ይህ መጽሐፍ ፈጣሪ የሰጠንን ችሎታና ማስተዋል ለበጎ ነገር ማዋል እንደምንችል የምንማርበት፣ ከየትኛውም ከባድ ውድቀት መነሳት እንደሚቻል የሚያሳይና የትውልድ ቅብብሎሽን የሚያጸና የታሪክ መዝገብ መሆኑን የደረሰን መረጃ ያመለክታል።
የመጽሐፉ የምረቃ ሥነ-ስርዓት ቅዳሜ ግንቦት 15 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ጀምሮ ከሜክስኮ ወደ መካኒሳ በሚወስደው መንገድ፣ ከሳር ቤት አደባባይ አለፍ ብሎ በስተቀኝ በኩል በሚገኘው የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቲዎሎጂካል ሴሚናሪ (EGST) አዳራሽ በድምቀት እንደሚካሄድ ታውቋል።
በዚህ ታላቅና ታሪካዊ የምረቃ በዓል ላይ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች፣ ወዳጅ ዘመዶችና የመጽሐፍ አፍቃሪያን ተገኝተው የደስታው ተካፋይ እንዲሆኑ አዘጋጆቹ በአክብሮት ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።
Sponsored by
Surafel
20 days ago
በቡታጅራ ከአንድ ቢሊየን ብር በላይ በሆነ ወጪ የተገነቡ ግዙፍ የልማት ፕሮጀክቶች በርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) ተመረቁ
***************************
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) በምሥራቅ ጉራጌ ዞን ቡታጅራ ከተማ የማኅበረሰቡን ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ፣ በአጭር ጊዜ በጥራት ግንባታቸው የተጠናቀቁ ልዩ ልዩ የልማት ፕሮጀክቶችን መርቀው ለአገልግሎት ክፍት አድርገዋል።
ተመርቀው ለአገልግሎት የበቁት እነዚህ ፕሮጀክቶች ከአንድ ቢሊየን ብር በላይ ወጪ የተደረገባቸው ሲሆን፣ ለቀጣይ ሥራዎች ውጤታማነት ትልቅ አቅም የሚፈጥሩ፣ የከተማዋን ልማትና ዕድገት እንዲሁም የሕዝቡን ተጠቃሚነት ከፍ የሚያደርጉ መሆናቸው ተገልጿል።
በርዕሰ መስተዳድሩ ተመርቀው ለአገልግሎት ከበቁት የልማት ፕሮጀክቶች መካከል የ 8 ነጥብ 35 ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት፣ የወንዝ ዳርቻ ፕሮጀክት፣ አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት፣ የማኅበረሰብ አቀፍ የሕዝብ መድኃኒት መደብር፣ የልጆች መዝናኛ ማዕከል፣ ሴራና ባህል ቤት፣ የንፁህ መጠጥ ውኃ ፕሮጀክት፣ የዋናው መንገድ ስማርት ፖል እንዲሁም መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ተጠቃሽ ናቸው።
ከዚህም በተጨማሪ በከተማዋ በቀጣይ ለሚገነቡ የጤና ጣቢያ እና የስታዲየም ግንባታ ማስጀመሪያ የሚሆን የመሠረተ ድንጋይ ተቀምጧል።
ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) በምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ እንደገለጹት፣ የቡታጅራ ከተማን ለነዋሪዎች ምቹ ለማድረግ የተጀመረው ጥረት የሚደነቅ ነው።
ከተማዋን አሁን በተጀመረው ፍጥነት ማሳደግ ከተቻለ የኢንቨስትመንትና የቱሪዝም ማዕከል እንደምትሆን ጽኑ እምነታቸውን የገለጹት ርዕሰ መስተዳድሩ፣ ቡታጅራ በብዝሃነት የደመቀች ከተማ መሆኗን ተከትሎ የሰላም ተምሳሌት በማድረግ ለመኖሪያ፣ ለንግድና ለኢንቨስትመንት ይበልጥ ተመራጭ እንድትሆን መሥራትና የከተማውን ገቢ አሟጦ በመጠቀም የልማት ፕሮጀክቶችን እውን ማድረግ እንደሚገባ አሳስበዋል።
በምረቃ መርሃ-ግብሩ ላይ የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት አቶ ኤርሲኖ አቡሬ፣ የምሥራቅ ጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሙስጠፋ ሐሰን፣ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የከተማ ልማትና ኢንዱስትሪ ክላስተር አስተባባሪና የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ ኃላፊ አቶ ስንታየሁ ወልደሚካኤልን ጨምሮ ሌሎች የክልል፣ የዞን፣ የከተማና የወረዳ አስተዳደር ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።
#ethiopia #butajira #development #centralethiopia #regionalnews
***************************
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) በምሥራቅ ጉራጌ ዞን ቡታጅራ ከተማ የማኅበረሰቡን ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ፣ በአጭር ጊዜ በጥራት ግንባታቸው የተጠናቀቁ ልዩ ልዩ የልማት ፕሮጀክቶችን መርቀው ለአገልግሎት ክፍት አድርገዋል።
ተመርቀው ለአገልግሎት የበቁት እነዚህ ፕሮጀክቶች ከአንድ ቢሊየን ብር በላይ ወጪ የተደረገባቸው ሲሆን፣ ለቀጣይ ሥራዎች ውጤታማነት ትልቅ አቅም የሚፈጥሩ፣ የከተማዋን ልማትና ዕድገት እንዲሁም የሕዝቡን ተጠቃሚነት ከፍ የሚያደርጉ መሆናቸው ተገልጿል።
በርዕሰ መስተዳድሩ ተመርቀው ለአገልግሎት ከበቁት የልማት ፕሮጀክቶች መካከል የ 8 ነጥብ 35 ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት፣ የወንዝ ዳርቻ ፕሮጀክት፣ አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት፣ የማኅበረሰብ አቀፍ የሕዝብ መድኃኒት መደብር፣ የልጆች መዝናኛ ማዕከል፣ ሴራና ባህል ቤት፣ የንፁህ መጠጥ ውኃ ፕሮጀክት፣ የዋናው መንገድ ስማርት ፖል እንዲሁም መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ተጠቃሽ ናቸው።
ከዚህም በተጨማሪ በከተማዋ በቀጣይ ለሚገነቡ የጤና ጣቢያ እና የስታዲየም ግንባታ ማስጀመሪያ የሚሆን የመሠረተ ድንጋይ ተቀምጧል።
ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) በምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ እንደገለጹት፣ የቡታጅራ ከተማን ለነዋሪዎች ምቹ ለማድረግ የተጀመረው ጥረት የሚደነቅ ነው።
ከተማዋን አሁን በተጀመረው ፍጥነት ማሳደግ ከተቻለ የኢንቨስትመንትና የቱሪዝም ማዕከል እንደምትሆን ጽኑ እምነታቸውን የገለጹት ርዕሰ መስተዳድሩ፣ ቡታጅራ በብዝሃነት የደመቀች ከተማ መሆኗን ተከትሎ የሰላም ተምሳሌት በማድረግ ለመኖሪያ፣ ለንግድና ለኢንቨስትመንት ይበልጥ ተመራጭ እንድትሆን መሥራትና የከተማውን ገቢ አሟጦ በመጠቀም የልማት ፕሮጀክቶችን እውን ማድረግ እንደሚገባ አሳስበዋል።
በምረቃ መርሃ-ግብሩ ላይ የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት አቶ ኤርሲኖ አቡሬ፣ የምሥራቅ ጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሙስጠፋ ሐሰን፣ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የከተማ ልማትና ኢንዱስትሪ ክላስተር አስተባባሪና የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ ኃላፊ አቶ ስንታየሁ ወልደሚካኤልን ጨምሮ ሌሎች የክልል፣ የዞን፣ የከተማና የወረዳ አስተዳደር ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።
#ethiopia #butajira #development #centralethiopia #regionalnews
27 days ago
ኑ ቡና ጠጡ
ጊዜ እያለፈብን እየመሰለኝ ነው!!!
ሀገሬ ከዳር እስከዳር ለምለም ናት የጎጃም ጤፍ መሸመት ፤የለቀምት ቡና፤የጉራጌው ክትፎ፤የአላባው በርበሬ፤የሆሳህናው ፍራፍሬ ፤የደቡቡ ውብ ስፍራ፤የአክሱም ፂዮን ፅላት፤የጎንደሩ ደብር፤የምስራቁ ፍቅር ከነ ሙሸበኩ ፤የኦሮሞው ገዳ ቂቤው ማሩ ኸረ ምኑ ቅጡ ሁሉም አልናፈቃችሁም???
ጎበዝ የተዘጋው መስመር ይከፈት እኔም አንተም አንቺም እንደ ሃገር ዋጋም ክብርም አለን። የሰላም የፍቅር እና የአብሮነት አፈሙዝ እናንሳ##
ሚዲያም የራሱ ስርዓት አለው በእውቀት ተደራጅተህ ሙሉ ፍቃድ እና አውንታዊ ምላሽ ከሚመለከተው አካል አግኝተህ የሃገሪቷ ህግ እና መመሪያ በሚፈቅደው መልኩ ብንጓዝ መስመር በሳቱ አጀንዳዎች የሰውን አምሮ እየገዙ የተሠሩትንም ሆነ ሊሠሩ የሚገቡትን እንደ ሃገር ሳናስተውል ከሆነ አካል ጋር ጊዜ እያለፈብን እየተራራቅን ነው።
እስቲ ሁላችንም በየእውቀታችን ሀገራችንን እናግዝ የሚሰሩ እጆችን እናመስግን የሚዘርፉ ልቦችን እናርም ሀገር በስልክ እንድትጠፋ አንፍቀድ የወጣቱ አቅም የምንጠቀምበት የኑሮ ውድነትን የምናረጋጋበት የተጀመሩትን ተጋግዘን የምንጨርስበት ሰላምን አንድነትን ተካፍሎ ተጋግዞ ማደግን እንስበክበት። እንደቀደመው በፍቅር ቡና ተጠራርተን ችግር እንፍታበት!! የተቸገረ እናግዝበት የወለደ እንጠይቅበት የተጣላ እናስታርቅበት ወደቀደመው ሶሻል ሚዲያ ቡና ጠጡ እንመለስ ባለን ትርፍ ግዜ እንማከር። ጎረቤት እንሞሽር የሞተ እንቅበር ከእሴቶቻችን አናፈንግጥ ለነገዋ ኢትዮጵያዊ ዛሬ እንስራ!!
ሁላችንም ወዳለን ፀጋችን እንመለስ የሚያፈርስ ሃሳብ ሁሌም ከራሳችን መፍረስ ይጀምራል። በስልኮቻችን ዘመድ እንጠይቅበት ቴክኖሎጂ እውቀት እንሸምትበት። የተሻሉ የሚበጁ የሚያፈርሱንን ሳይሆን የሚገነቡንን ሃሳብ እናካፍልበት!!!
ፍትህ የተረጋጋ ሰላም ያላት ኢትዮጵያን የምንናፍቅ የልጆቻችንን ኢትዮጵያ እንገንባ። በመመካከር በውይይት እና በፍቅር እንገዛ ሀገሬ ጀግና ገበሬ ታታሪ ወጣት የበቁ የነቁ ምሁሮች ነገን የሚናፍቁ የባለራዕይ ትውልዶች አሏት!! ስለምን ደነዘዝን ስለምንስ ላሉባልታ ተረታን እስቲ ከሰው ጓዳ ወጥተን ወደ ስለራስ መለወጥ እንትጋ በወሬ ወለደ ወሬ ሀገር አናደንቁር!!!
ግድ የለም እድል ስጡን ሁላችንም በየሞያችን ሀገር እናቅና ነጋዴው ይነግድ ገበሬውም ይረስ መምህሩም ትውልድ ያፍራ መበልፀግ ባለተራነት ሳይሆን የጋራ መደመር ከሆነ ሜዳው ለሁላችን ክፍት ከሆነ ይህ በስራ ማጣት በሶሻል ሚዲያ ርሃብ የተጎዳን ዜጋ ሰው ተኮር በሆኑ ስራዎችም እንካሰው!!!
አለምን ያስደመመ የክብር ኖቤል ለሃገር አያንስም በየቀጠናዎቹ እንደከዚህ ቀደሙ የነዋሪው ፎረም ስለነዋሪው ይሞግት የወጣት አደረጃጀቶች ለሰፊው ወጣት ዘብ ይቁም ከፎቶ የዘለለ ስራ መሬት የወረደ ተጨባጭ ለውጥ እንደኮሊደሮቻችን ያስመዝግብ የፍትህ እና የህግ አካሉ በመረጃ እና በማስረጃ በተጨበጠ መረጃ ፍትህ ያስፍንልን ዜጎቻችን በግለሰቦች አስተሳሰብ እና ጥላቻ ብቻ ደማቸው አይፍሰስ ሀገር በግለሰቦች አትለካም ሀገር መለኪያዋ እልፍ ነው።
በብዙ ቢሊዮን ዶላር የተገነቡ ኢንዱስቲሪዎቻችን ሁሉንም ዜጋ በእኩልነት ያስተናግዱ ያኔ በሰፈር አጀንዳ የማይጠመድ ትውልድ እናተርፋለን!!!
የፍትህ አካሉንም በጥበብ እናግዝ በየስልኩ እየወጣን ባልተረጋገጠ መረጃ ሰው አንዝለፍ ያለበለዚያ የሃገሬ የፍትህ እና የህግ አካል ላይ ትልቅ ጥያቄ ሊኖረኝ ነው ፍትህ እና ህግ በመንደር አሉባልታ ሳይሆን በመረጃ እና ማስረጃ እንደሚፈታ እናስተውል።
መልካም ሰንበት ኑ ቡና ጠጡ!!!
በይድነቃቸው አለኝታ
ጊዜ እያለፈብን እየመሰለኝ ነው!!!
ሀገሬ ከዳር እስከዳር ለምለም ናት የጎጃም ጤፍ መሸመት ፤የለቀምት ቡና፤የጉራጌው ክትፎ፤የአላባው በርበሬ፤የሆሳህናው ፍራፍሬ ፤የደቡቡ ውብ ስፍራ፤የአክሱም ፂዮን ፅላት፤የጎንደሩ ደብር፤የምስራቁ ፍቅር ከነ ሙሸበኩ ፤የኦሮሞው ገዳ ቂቤው ማሩ ኸረ ምኑ ቅጡ ሁሉም አልናፈቃችሁም???
ጎበዝ የተዘጋው መስመር ይከፈት እኔም አንተም አንቺም እንደ ሃገር ዋጋም ክብርም አለን። የሰላም የፍቅር እና የአብሮነት አፈሙዝ እናንሳ##
ሚዲያም የራሱ ስርዓት አለው በእውቀት ተደራጅተህ ሙሉ ፍቃድ እና አውንታዊ ምላሽ ከሚመለከተው አካል አግኝተህ የሃገሪቷ ህግ እና መመሪያ በሚፈቅደው መልኩ ብንጓዝ መስመር በሳቱ አጀንዳዎች የሰውን አምሮ እየገዙ የተሠሩትንም ሆነ ሊሠሩ የሚገቡትን እንደ ሃገር ሳናስተውል ከሆነ አካል ጋር ጊዜ እያለፈብን እየተራራቅን ነው።
እስቲ ሁላችንም በየእውቀታችን ሀገራችንን እናግዝ የሚሰሩ እጆችን እናመስግን የሚዘርፉ ልቦችን እናርም ሀገር በስልክ እንድትጠፋ አንፍቀድ የወጣቱ አቅም የምንጠቀምበት የኑሮ ውድነትን የምናረጋጋበት የተጀመሩትን ተጋግዘን የምንጨርስበት ሰላምን አንድነትን ተካፍሎ ተጋግዞ ማደግን እንስበክበት። እንደቀደመው በፍቅር ቡና ተጠራርተን ችግር እንፍታበት!! የተቸገረ እናግዝበት የወለደ እንጠይቅበት የተጣላ እናስታርቅበት ወደቀደመው ሶሻል ሚዲያ ቡና ጠጡ እንመለስ ባለን ትርፍ ግዜ እንማከር። ጎረቤት እንሞሽር የሞተ እንቅበር ከእሴቶቻችን አናፈንግጥ ለነገዋ ኢትዮጵያዊ ዛሬ እንስራ!!
ሁላችንም ወዳለን ፀጋችን እንመለስ የሚያፈርስ ሃሳብ ሁሌም ከራሳችን መፍረስ ይጀምራል። በስልኮቻችን ዘመድ እንጠይቅበት ቴክኖሎጂ እውቀት እንሸምትበት። የተሻሉ የሚበጁ የሚያፈርሱንን ሳይሆን የሚገነቡንን ሃሳብ እናካፍልበት!!!
ፍትህ የተረጋጋ ሰላም ያላት ኢትዮጵያን የምንናፍቅ የልጆቻችንን ኢትዮጵያ እንገንባ። በመመካከር በውይይት እና በፍቅር እንገዛ ሀገሬ ጀግና ገበሬ ታታሪ ወጣት የበቁ የነቁ ምሁሮች ነገን የሚናፍቁ የባለራዕይ ትውልዶች አሏት!! ስለምን ደነዘዝን ስለምንስ ላሉባልታ ተረታን እስቲ ከሰው ጓዳ ወጥተን ወደ ስለራስ መለወጥ እንትጋ በወሬ ወለደ ወሬ ሀገር አናደንቁር!!!
ግድ የለም እድል ስጡን ሁላችንም በየሞያችን ሀገር እናቅና ነጋዴው ይነግድ ገበሬውም ይረስ መምህሩም ትውልድ ያፍራ መበልፀግ ባለተራነት ሳይሆን የጋራ መደመር ከሆነ ሜዳው ለሁላችን ክፍት ከሆነ ይህ በስራ ማጣት በሶሻል ሚዲያ ርሃብ የተጎዳን ዜጋ ሰው ተኮር በሆኑ ስራዎችም እንካሰው!!!
አለምን ያስደመመ የክብር ኖቤል ለሃገር አያንስም በየቀጠናዎቹ እንደከዚህ ቀደሙ የነዋሪው ፎረም ስለነዋሪው ይሞግት የወጣት አደረጃጀቶች ለሰፊው ወጣት ዘብ ይቁም ከፎቶ የዘለለ ስራ መሬት የወረደ ተጨባጭ ለውጥ እንደኮሊደሮቻችን ያስመዝግብ የፍትህ እና የህግ አካሉ በመረጃ እና በማስረጃ በተጨበጠ መረጃ ፍትህ ያስፍንልን ዜጎቻችን በግለሰቦች አስተሳሰብ እና ጥላቻ ብቻ ደማቸው አይፍሰስ ሀገር በግለሰቦች አትለካም ሀገር መለኪያዋ እልፍ ነው።
በብዙ ቢሊዮን ዶላር የተገነቡ ኢንዱስቲሪዎቻችን ሁሉንም ዜጋ በእኩልነት ያስተናግዱ ያኔ በሰፈር አጀንዳ የማይጠመድ ትውልድ እናተርፋለን!!!
የፍትህ አካሉንም በጥበብ እናግዝ በየስልኩ እየወጣን ባልተረጋገጠ መረጃ ሰው አንዝለፍ ያለበለዚያ የሃገሬ የፍትህ እና የህግ አካል ላይ ትልቅ ጥያቄ ሊኖረኝ ነው ፍትህ እና ህግ በመንደር አሉባልታ ሳይሆን በመረጃ እና ማስረጃ እንደሚፈታ እናስተውል።
መልካም ሰንበት ኑ ቡና ጠጡ!!!
በይድነቃቸው አለኝታ
1 month ago
#ethiopia | በአዲስ አበባ የተፈፀመ ጭካኔ | በጉራጌ ዞን የቀጠለው ጥቃት | ሆርሙዝ የአሜሪካና ቻይና የሰላም በር
" target="_blank" class="inline-link">https://new-en.yenevibe.co...
" target="_blank" class="inline-link">https://new-en.yenevibe.co...
1 month ago
የአንድ ቤተሰብ አባላትን ጨምሮ አምስት ሰዎች ተገደሉ
#fastmereja I በምሥራቅ ጉራጌ ዞን ታጣቂዎች በመኖሪያ ቤት ውስጥ በከፈቱት ተኩስ እናት ከሦስት ልጆቿ ጋር መገደላቸውን ዶይቼ ቬለ ዘገበ።
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምሥራቅ ጉራጌ ዞን ምሥራቅ መስቃን ወረዳ በደረሰ የታጣቂዎች ጥቃት አምስት ሰዎች ሕይወታቸውን አጥተዋል። ዶይቼ ቬለ እንደዘገበው ጥቃቱ የተፈጸመው በኢንሴኖ ከተማ "አየር ጤና" ተብሎ በሚጠራው ሰፈር ሲሆን፣ ታጣቂዎቹ ተጎጂዎቹ ተኝተው በነበሩበት መኖሪያ ቤት ውስጥ በመግባት ተኩስ መክፈታቸውን የአይን እማኞች እና የሟች ዘመዶች ገልጸዋል።
ከሟቾቹ መካከል አራቱ የአንድ ቤተሰብ አባላት (እናትና ሦስት ልጆቿ) መሆናቸው ተረጋግጧል። ታጣቂዎቹ ወደ መንደሩ እየተኮሱ በመግባት ጥቃቱን ፈጽመው ወዲያውኑ ከአካባቢው መሰወራቸውን ዘገባው አመልክቷል። ጥቃት አድራሾቹ በአካባቢው በሽፍትነት የሚንቀሳቀሱ ወጣቶች ሳይሆኑ እንደማይቀሩ ነዋሪዎች መግለጻቸውን ዘገባው ጠቅሷል።
#fastmereja I በምሥራቅ ጉራጌ ዞን ታጣቂዎች በመኖሪያ ቤት ውስጥ በከፈቱት ተኩስ እናት ከሦስት ልጆቿ ጋር መገደላቸውን ዶይቼ ቬለ ዘገበ።
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምሥራቅ ጉራጌ ዞን ምሥራቅ መስቃን ወረዳ በደረሰ የታጣቂዎች ጥቃት አምስት ሰዎች ሕይወታቸውን አጥተዋል። ዶይቼ ቬለ እንደዘገበው ጥቃቱ የተፈጸመው በኢንሴኖ ከተማ "አየር ጤና" ተብሎ በሚጠራው ሰፈር ሲሆን፣ ታጣቂዎቹ ተጎጂዎቹ ተኝተው በነበሩበት መኖሪያ ቤት ውስጥ በመግባት ተኩስ መክፈታቸውን የአይን እማኞች እና የሟች ዘመዶች ገልጸዋል።
ከሟቾቹ መካከል አራቱ የአንድ ቤተሰብ አባላት (እናትና ሦስት ልጆቿ) መሆናቸው ተረጋግጧል። ታጣቂዎቹ ወደ መንደሩ እየተኮሱ በመግባት ጥቃቱን ፈጽመው ወዲያውኑ ከአካባቢው መሰወራቸውን ዘገባው አመልክቷል። ጥቃት አድራሾቹ በአካባቢው በሽፍትነት የሚንቀሳቀሱ ወጣቶች ሳይሆኑ እንደማይቀሩ ነዋሪዎች መግለጻቸውን ዘገባው ጠቅሷል።
1 month ago
ሚያዝያ 24/25 በድምቀት ይመረቃል
ማረፊያና ማለፊያው ደብር
በጉራጌ ምድር ጠርዙን ይዞ የቆመው የምሁር ኢየሱስ ገዳም፣ ከምድራዊው ዓለም ይልቅ ወደ ሰማያዊው መንግሥት የቀረበ ይመስላል።
ወደ ቅጽረ ግቢው ሲዘልቁ ነፍስን የሚያረሰርሱ፣ ሥጋን የሚያሳርፉ ድንቅ ትዕይንቶች በፊቱ ይዘረጋሉ።
ጥንታውያንና ግርማ ሞገስ የተላበሱት የገዳሙ ዛፎች፣ እንደ ዘበኛ ቆመው ጥላን ይግታሉ። ነፋሱ በቅጠሎቻቸው መካከል ሲያልፍ የሚፈጥረው "ሹክሹክታ" ለፀሎት የሚጋብዝ ረቂቅ ድምፅ አለው።
በቅርንጫፎቹ ላይ የሚረግጡት አእዋፍ፣ ለፈጣሪ ምስጋና የሚያቀርቡ ይመስል በልዩ ዜማቸው የገዳሙን ሰላም ያደምቁታል። ዝማሬያቸው ከገዳሙ መንፈሳዊነት ጋር ተዋህዶ የነፍስ ምግብ ይሆናል።
የገዳሙ አቀማመጥና የሕንፃው ጥበብ የአባቶቻችንን የታሪክ አሻራ በጉልህ ያሳያል። ከሩቅ ሲታይ የማማው ግርማ፣ በውስጥ ሲታይ ደግሞ የቅድስናው ድባብ የሰው ልጅን ልብ በአድናቆት ይሞላል።
በዚያ የተቀደሰ ስፍራ የካህናቱ ዝማሬ ሲሰማ፣ ምድራዊው ድምፅ ጠፍቶ ሰማያዊ ዜማ የተጀመረ ይመስላል። በጥበብና በትሕትና የተሞላው አስተምሯቸው ደግሞ የጠፋውን የሚመልስ፣ የደከመውን የሚያጸና የመንፈስ ብርሃን ነው።
ምሁር ኢየሱስ ገዳም ተፈጥሮ ከፈጣሪዋ ጋር የተገናኘችበት፣ ሰው ከራሱ ጋር የታረቀበት፣ በቅድስናና በውበት የተከበበ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የከበረ ዕንቁ ነው።
ለዚህ ምረቃ በዓል መብቃት እንደ ፀሃይ ብርሃን ነው። አንድም ጠዋት ሁለትም ቀትር ሆኖ ፍንትው ብሎ መታየት።
ምንጭ 👉እንዳልካቸው ደሳለኝ
ያለን ቦታ ጥቂት ነው ፈጥነው ይመዝገቡ
አዘጋጅ ምሁር ኢየሱስ ገዳም
ቅዱስ ዳዊት የበገና ቤተሰብ ጋር ይጓዙ
0911358560/0911083713
0921327074 /0913383033
ማረፊያና ማለፊያው ደብር
በጉራጌ ምድር ጠርዙን ይዞ የቆመው የምሁር ኢየሱስ ገዳም፣ ከምድራዊው ዓለም ይልቅ ወደ ሰማያዊው መንግሥት የቀረበ ይመስላል።
ወደ ቅጽረ ግቢው ሲዘልቁ ነፍስን የሚያረሰርሱ፣ ሥጋን የሚያሳርፉ ድንቅ ትዕይንቶች በፊቱ ይዘረጋሉ።
ጥንታውያንና ግርማ ሞገስ የተላበሱት የገዳሙ ዛፎች፣ እንደ ዘበኛ ቆመው ጥላን ይግታሉ። ነፋሱ በቅጠሎቻቸው መካከል ሲያልፍ የሚፈጥረው "ሹክሹክታ" ለፀሎት የሚጋብዝ ረቂቅ ድምፅ አለው።
በቅርንጫፎቹ ላይ የሚረግጡት አእዋፍ፣ ለፈጣሪ ምስጋና የሚያቀርቡ ይመስል በልዩ ዜማቸው የገዳሙን ሰላም ያደምቁታል። ዝማሬያቸው ከገዳሙ መንፈሳዊነት ጋር ተዋህዶ የነፍስ ምግብ ይሆናል።
የገዳሙ አቀማመጥና የሕንፃው ጥበብ የአባቶቻችንን የታሪክ አሻራ በጉልህ ያሳያል። ከሩቅ ሲታይ የማማው ግርማ፣ በውስጥ ሲታይ ደግሞ የቅድስናው ድባብ የሰው ልጅን ልብ በአድናቆት ይሞላል።
በዚያ የተቀደሰ ስፍራ የካህናቱ ዝማሬ ሲሰማ፣ ምድራዊው ድምፅ ጠፍቶ ሰማያዊ ዜማ የተጀመረ ይመስላል። በጥበብና በትሕትና የተሞላው አስተምሯቸው ደግሞ የጠፋውን የሚመልስ፣ የደከመውን የሚያጸና የመንፈስ ብርሃን ነው።
ምሁር ኢየሱስ ገዳም ተፈጥሮ ከፈጣሪዋ ጋር የተገናኘችበት፣ ሰው ከራሱ ጋር የታረቀበት፣ በቅድስናና በውበት የተከበበ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የከበረ ዕንቁ ነው።
ለዚህ ምረቃ በዓል መብቃት እንደ ፀሃይ ብርሃን ነው። አንድም ጠዋት ሁለትም ቀትር ሆኖ ፍንትው ብሎ መታየት።
ምንጭ 👉እንዳልካቸው ደሳለኝ
ያለን ቦታ ጥቂት ነው ፈጥነው ይመዝገቡ
አዘጋጅ ምሁር ኢየሱስ ገዳም
ቅዱስ ዳዊት የበገና ቤተሰብ ጋር ይጓዙ
0911358560/0911083713
0921327074 /0913383033
Sponsored by
Surafel
1 month ago
በምሥራቅ ጉራጌ ዞን አምስት ሰዎች በታጣቂዎች ተገደሉ!
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምሥራቅ ጉራጌ ዞን ምሥራቅ መስቃን ወረዳ አራት የአንድ ቤተሰብ አባላትን ጨምሮ አምስት ሰዎች በታጣቂች ተገደሉ።ታጣቂዎቹ ጥቃቱን ያደረሱት ትናንት ከሌሊቱ 9 ሰዓት ላይ በተኙበት ገብተው መሣሪያ በመተኮስ መሆኑን የአካባቢው ነዋሪዎች እና የሟች ዘመዶች ለዶቼ ቬሌ ተናግረዋል፡፡
ጥቃቱ የተፈጸመው በወረዳ ኢንሴኖ በተባለ ከተማ ውስጥ መሆኑን ለዶቼ ቬለ የተናገሩ አንድ የሟች የቅርብ ዘመድ «ታጣቂዎቹ በተለምዶ አየር ጤና ተብሎ በሚጠራው መንደር እየተኮሱ ነው የገቡት፡፡ወደ መኖሪያ ቤት በመግባት አምስት ሰዎችን ተኩሰው ከገደሉ በኋላ ተመልሰው ሄደዋል፡፡ከሟቾቹ መካከል አራቱ የአንድ ቤተሰብ አባላት የሆኑ እናት ከሦስት ልጆቿ ጋር ነው» ብለዋል ፡፡
በከተማው ነዋሪ የሆኑ ሌላ የዐይን አማኝ በበኩላቸው ግድያው መፈጸሙን አረጋግጠው ጥቃት አድራሾቹ በአካባቢው በሽፍትነት የሚንቀሳቀሱ ወጣቶች ሳይሆኑ እንዳልቀረ ተናግረዋል፡፡ዶቼ ቬለ ጥቃቱን በተመለከተ ለማነጋገር በስልክ ያገኛቸው የምሥራቅ መስቃን ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ መሀመድ ሰረላ መረጃውን አሰባስበው እንደሚገልጹ ቀጠሮ ይዘው ነበር፡፡ነገር ግን በቀጠሮው ሰዓት ሥልካቸው ዝግ በመሆኑ ምላሻቸውን ማካተት አልተቻለም፡፡
Via DW
seledadotio
seledadotio
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምሥራቅ ጉራጌ ዞን ምሥራቅ መስቃን ወረዳ አራት የአንድ ቤተሰብ አባላትን ጨምሮ አምስት ሰዎች በታጣቂች ተገደሉ።ታጣቂዎቹ ጥቃቱን ያደረሱት ትናንት ከሌሊቱ 9 ሰዓት ላይ በተኙበት ገብተው መሣሪያ በመተኮስ መሆኑን የአካባቢው ነዋሪዎች እና የሟች ዘመዶች ለዶቼ ቬሌ ተናግረዋል፡፡
ጥቃቱ የተፈጸመው በወረዳ ኢንሴኖ በተባለ ከተማ ውስጥ መሆኑን ለዶቼ ቬለ የተናገሩ አንድ የሟች የቅርብ ዘመድ «ታጣቂዎቹ በተለምዶ አየር ጤና ተብሎ በሚጠራው መንደር እየተኮሱ ነው የገቡት፡፡ወደ መኖሪያ ቤት በመግባት አምስት ሰዎችን ተኩሰው ከገደሉ በኋላ ተመልሰው ሄደዋል፡፡ከሟቾቹ መካከል አራቱ የአንድ ቤተሰብ አባላት የሆኑ እናት ከሦስት ልጆቿ ጋር ነው» ብለዋል ፡፡
በከተማው ነዋሪ የሆኑ ሌላ የዐይን አማኝ በበኩላቸው ግድያው መፈጸሙን አረጋግጠው ጥቃት አድራሾቹ በአካባቢው በሽፍትነት የሚንቀሳቀሱ ወጣቶች ሳይሆኑ እንዳልቀረ ተናግረዋል፡፡ዶቼ ቬለ ጥቃቱን በተመለከተ ለማነጋገር በስልክ ያገኛቸው የምሥራቅ መስቃን ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ መሀመድ ሰረላ መረጃውን አሰባስበው እንደሚገልጹ ቀጠሮ ይዘው ነበር፡፡ነገር ግን በቀጠሮው ሰዓት ሥልካቸው ዝግ በመሆኑ ምላሻቸውን ማካተት አልተቻለም፡፡
Via DW
seledadotio
seledadotio
1 month ago
ቅዳሴ ቤቱ ለምሁር ኢየሱስ ገዳም
የቤተክርስቲያን የምረቅታት ጉዞ
#ethiopia | የምሁር ገዳመ ኢየሱስ ታሪክ በአጭሩ
በሀገራችን ከሚገኙ ቅዱሳት መካናት መካከል ምሁር የኢየሱስ ገዳም አንዱ ነው ።
በጅማ በር ወልቂጤ በኩል ከአዲስ አበባ 210 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በሰባት ቤት ጉራጌ በምሁርና አክሊል ወረዳ ይገኛል ። ምሁር የኢየሱስ ገዳም የተመሰረተው ከዮዲት ዘመን /ከ840 ዓ .ም / በፊት ሲሆን በደቡብ የሀገራችን ክፍል ከሚገኙ ገዳማት አንጋፋና ጥንታዊ ገዳም ነው።
ሀገረ ምሁር መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከእመቤታችን ጋር በተሰደደ ጊዜ ከባረካቸው የኢትዮዽያ ግዛቶች አንዱ መሆኑ በድርሳነ ዑራኤል ላይ ተገልጿል።
የምሁር ገዳም ኢየሱስ ቤተክርስቲያን በደብርነት የተተከለው በ9 ኛው መቶ ክፍለ ዘመን እንደሆነ እንግለፅ እንጂ ቦታው የተገደመው በጻድቁ አቡነ ዜና ማርቆስ በ13ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ነው
ከጻድቁ አባታችን ዜና ማርቆስ ገድል እንደምንረዳው አባታችን ዜና ማርቆስ በእግዚአብሔር ፍቃድ “ሑር ሀገረ ምሁር” ወደ ምሁር ሀገር ሂድ ተብለው ደመና ጠቅሰው ወደ ምሁር በመጡ ጊዜ የምሁር ሰዎች ከአምልኮተ እግዚአብሔር ርቀው በጣኦት ያመልኩ ነበር ።
አቡነ ዜና ማርቆስ ወደ ምሁር ባደረጉት የመጀመሪያ ሐዋሪያዊ ጉዞ በወንጌል ትምህርትና በገቢረ ተአምር የምሁርን ሰዎች ከአምልኮተ ጣኦት ወደ ቀደመ አባቶቻቸው ሃይማኖት ወደ አምልኮተ እግዚአብሔር መልስው በቀናች የክርስትና ሃይማኖት እንዲፀኑ እያስተማሩ 3 አመት በምሁር ተቀምጠዋል።
ከዚህ በኋላ ጻድቅና ቅዱስ ሐዋርያው አባታችን ዜና ማርቆስ ከምሁር ወደ ሌሎቹ የጉራጌ ግዛቶችና የተለያዩ የሀገራችን አካባቢ ተዘዋውረው ወንጌልን ሲያስተምሩ ቆይተውከሁለት ዓመታት ቆይታ በኃላ በውቅቱ ከነበሩት ግብጻዊ የኢትዮዽያ ዻዻስ አባ
[30/04, 13:29] Biruk Seiyfu - Muhur Gedam: ቄርሎስ ጋር ወደ ምሁር ለሁለተኛ ጊዜ መጡ ።
አባታችን ዜና ማርቆስ በሁለተኛው ጉዛቸው ነው የምሁር ኢየሱስ ገዳምን መሀሉ ገነት ዳሩ እሳት ይሁን ብለው የገደሙት።
ምሁር የ 44ቱ ታቦታት ሀገር ተብሎ ይጠራል ።
ምሁር የ44ቱ ታቦት ሀገር ተብሎ የሚጠራው በገዳሙ ባሉት ታቦታት ነው እንጂ በሀገረ ምሁር የተተከሉት አብያተ ክርስቲያናት 44 ብቻ አይደሉም።
መጃውን ያደረሰን 👉Biruk Seifu
በገዳሙ ጉዞ ለመጓዝ
ከታች ባለው ስልክ ቁጥር ይመዝገቡ
0911083713/0913383033/0911358560
የቤተክርስቲያን የምረቅታት ጉዞ
#ethiopia | የምሁር ገዳመ ኢየሱስ ታሪክ በአጭሩ
በሀገራችን ከሚገኙ ቅዱሳት መካናት መካከል ምሁር የኢየሱስ ገዳም አንዱ ነው ።
በጅማ በር ወልቂጤ በኩል ከአዲስ አበባ 210 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በሰባት ቤት ጉራጌ በምሁርና አክሊል ወረዳ ይገኛል ። ምሁር የኢየሱስ ገዳም የተመሰረተው ከዮዲት ዘመን /ከ840 ዓ .ም / በፊት ሲሆን በደቡብ የሀገራችን ክፍል ከሚገኙ ገዳማት አንጋፋና ጥንታዊ ገዳም ነው።
ሀገረ ምሁር መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከእመቤታችን ጋር በተሰደደ ጊዜ ከባረካቸው የኢትዮዽያ ግዛቶች አንዱ መሆኑ በድርሳነ ዑራኤል ላይ ተገልጿል።
የምሁር ገዳም ኢየሱስ ቤተክርስቲያን በደብርነት የተተከለው በ9 ኛው መቶ ክፍለ ዘመን እንደሆነ እንግለፅ እንጂ ቦታው የተገደመው በጻድቁ አቡነ ዜና ማርቆስ በ13ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ነው
ከጻድቁ አባታችን ዜና ማርቆስ ገድል እንደምንረዳው አባታችን ዜና ማርቆስ በእግዚአብሔር ፍቃድ “ሑር ሀገረ ምሁር” ወደ ምሁር ሀገር ሂድ ተብለው ደመና ጠቅሰው ወደ ምሁር በመጡ ጊዜ የምሁር ሰዎች ከአምልኮተ እግዚአብሔር ርቀው በጣኦት ያመልኩ ነበር ።
አቡነ ዜና ማርቆስ ወደ ምሁር ባደረጉት የመጀመሪያ ሐዋሪያዊ ጉዞ በወንጌል ትምህርትና በገቢረ ተአምር የምሁርን ሰዎች ከአምልኮተ ጣኦት ወደ ቀደመ አባቶቻቸው ሃይማኖት ወደ አምልኮተ እግዚአብሔር መልስው በቀናች የክርስትና ሃይማኖት እንዲፀኑ እያስተማሩ 3 አመት በምሁር ተቀምጠዋል።
ከዚህ በኋላ ጻድቅና ቅዱስ ሐዋርያው አባታችን ዜና ማርቆስ ከምሁር ወደ ሌሎቹ የጉራጌ ግዛቶችና የተለያዩ የሀገራችን አካባቢ ተዘዋውረው ወንጌልን ሲያስተምሩ ቆይተውከሁለት ዓመታት ቆይታ በኃላ በውቅቱ ከነበሩት ግብጻዊ የኢትዮዽያ ዻዻስ አባ
[30/04, 13:29] Biruk Seiyfu - Muhur Gedam: ቄርሎስ ጋር ወደ ምሁር ለሁለተኛ ጊዜ መጡ ።
አባታችን ዜና ማርቆስ በሁለተኛው ጉዛቸው ነው የምሁር ኢየሱስ ገዳምን መሀሉ ገነት ዳሩ እሳት ይሁን ብለው የገደሙት።
ምሁር የ 44ቱ ታቦታት ሀገር ተብሎ ይጠራል ።
ምሁር የ44ቱ ታቦት ሀገር ተብሎ የሚጠራው በገዳሙ ባሉት ታቦታት ነው እንጂ በሀገረ ምሁር የተተከሉት አብያተ ክርስቲያናት 44 ብቻ አይደሉም።
መጃውን ያደረሰን 👉Biruk Seifu
በገዳሙ ጉዞ ለመጓዝ
ከታች ባለው ስልክ ቁጥር ይመዝገቡ
0911083713/0913383033/0911358560
3 months ago
በአፍሪካ ግዙፍ ሪፈራል ሆስፒታል በጮቢ በዓታ ለማርያም ገዳም ሊገነባ ነው።
#fastmereja I በምሥራቅ ጉራጌ የሚገኘው የመካነ ሕይወት ጮቢ በዓታ ለማርያም አንድነት ገዳም፣ ባለፉት 20 ዓመታት በመንፈሳዊም ሆነ በልማት ዘርፍ አስደናቂ ውጤቶችን አስመዝግቧል።
ከ3,000 በላይ ሕፃናትን በመደበኛና በመንፈሳዊ ትምህርት አሳድጓል። ግዙፍ ባለ 8 ፎቅ ርዝመት ያለው ቤተ መቅደስ፣ 8 ኪ.ሜ መንገድ እና የ300 ሺህ ሊትር የውሃ ፕሮጀክት ገንብቷል። በ100 ሄክታር እርሻና በዘመናዊ የወተት ልማት አካባቢውን እየጠቀመ ይገኛል።
ገዳሙ አሁን ደግሞ 1,088 አልጋዎች ያሉትና በአፍሪካ ግዙፍ የተባለውን ሪፈራል ሆስፒታል ግንባታ ጀምሯል! ይህ ፕሮጀክት የሀገራችንን የጤና ችግር ከመቅረፍ ባለፈ ለሕክምና ወደ ውጭ የሚወጣውን ወጪ ያስቀራል ተብሏል።
ሆስፒታሉ በውስጡ ኮሌጅ፣ የህክምና ባለሙያዎች ማረፊያ ከሩቅ ቦታ ለሚምጡ የተመላላሽ ታካሚ ፣ አስታማሚዎች ሆቴሎች እና የተለያዩ ከህክምና ጋር የሚገናኙ ህንጻዎችን ጭምር አካቶ የያዘ ነው ተብሏል።
ሆስፒታሉን ገንብቶ ለማጠናቀቀ ከ1.5 እስከ 2 ቢሊዮን ብር እንደሚያስፈልገ የተነገረ ሲሆን በሰባት አመት ገንብቶ ለማጠናቀቀ እቅድ ተይዟል።
ይህንን ታላቅ ፕሮጀክት ለማጠናቀቅ የካቲት 29 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 10፡00 ጀምሮ ከዮድ አቢሲኒያ ሆቴል (ጉርድ ሾላ) የገቢ ማሰባሰቢያ ቀጥታ ስርጭት ፕሮግራም ተዘጋጅቷል።
የባንክ አካውንቶች፦
ንግድ ባንክ፦ 1000571767434
ወጋገን ባንክ፦ 1125179830101
አሃዱ ባንክ፦ 0000020010901
Zelle: +1(310)462 0185 (ኪሩቤል ጌታቸው)
ለተጨማሪ መረጃ 0903280707 / 0913569435
#fastmereja I በምሥራቅ ጉራጌ የሚገኘው የመካነ ሕይወት ጮቢ በዓታ ለማርያም አንድነት ገዳም፣ ባለፉት 20 ዓመታት በመንፈሳዊም ሆነ በልማት ዘርፍ አስደናቂ ውጤቶችን አስመዝግቧል።
ከ3,000 በላይ ሕፃናትን በመደበኛና በመንፈሳዊ ትምህርት አሳድጓል። ግዙፍ ባለ 8 ፎቅ ርዝመት ያለው ቤተ መቅደስ፣ 8 ኪ.ሜ መንገድ እና የ300 ሺህ ሊትር የውሃ ፕሮጀክት ገንብቷል። በ100 ሄክታር እርሻና በዘመናዊ የወተት ልማት አካባቢውን እየጠቀመ ይገኛል።
ገዳሙ አሁን ደግሞ 1,088 አልጋዎች ያሉትና በአፍሪካ ግዙፍ የተባለውን ሪፈራል ሆስፒታል ግንባታ ጀምሯል! ይህ ፕሮጀክት የሀገራችንን የጤና ችግር ከመቅረፍ ባለፈ ለሕክምና ወደ ውጭ የሚወጣውን ወጪ ያስቀራል ተብሏል።
ሆስፒታሉ በውስጡ ኮሌጅ፣ የህክምና ባለሙያዎች ማረፊያ ከሩቅ ቦታ ለሚምጡ የተመላላሽ ታካሚ ፣ አስታማሚዎች ሆቴሎች እና የተለያዩ ከህክምና ጋር የሚገናኙ ህንጻዎችን ጭምር አካቶ የያዘ ነው ተብሏል።
ሆስፒታሉን ገንብቶ ለማጠናቀቀ ከ1.5 እስከ 2 ቢሊዮን ብር እንደሚያስፈልገ የተነገረ ሲሆን በሰባት አመት ገንብቶ ለማጠናቀቀ እቅድ ተይዟል።
ይህንን ታላቅ ፕሮጀክት ለማጠናቀቅ የካቲት 29 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 10፡00 ጀምሮ ከዮድ አቢሲኒያ ሆቴል (ጉርድ ሾላ) የገቢ ማሰባሰቢያ ቀጥታ ስርጭት ፕሮግራም ተዘጋጅቷል።
የባንክ አካውንቶች፦
ንግድ ባንክ፦ 1000571767434
ወጋገን ባንክ፦ 1125179830101
አሃዱ ባንክ፦ 0000020010901
Zelle: +1(310)462 0185 (ኪሩቤል ጌታቸው)
ለተጨማሪ መረጃ 0903280707 / 0913569435
3 months ago
“ብራንዴ ተሰርቋል” በሚል ጃምቦ ኮንስትራክሽን በጀንቦሮ ሪል እስቴት ላይ የ1 ሚሊዮን ብር ክስ መሰረተ
በኢትዮጵያ የኮንስትራክሽንና የሪል እስቴት ኢንዱስትሪ ውስጥ ለሦስት አሥርተ ዓመታት ገደማ ስሙን የገነባው ጃምቦ ኮንስትራክሽን፣ አዲስ ወደ ገበያው በገባው ጀንቦሮ ሪል እስቴት ላይ የንግድ ምልክት ስያሜዬን ወስዶብኛል በሚል የ1 ሚሊዮን ብር የካሳ ክስ በፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት መሰረተ።
ጃምቦ ኮንስትራክሽን ለፍርድ ቤቱ ባቀረበው አቤቱታ፣ "ጀንቦሮ" የሚለው ስያሜ ከራሱ የንግድ ምልክት ጋር በድምፅ፣ በፊደላት አጻጻፍና በቃና ተመሳሳይነት ስላለው ደንበኞችንና ሚዲያን እያደናገረ ይገኛል ብሏል። ድርጅቱ ይህን ድርጊት "የብራንድ ነጠቃ" ሲል የገለጸው ሲሆን፣ በዚህም ምክንያት 1 ሚሊዮን ብር የሚገመት የገንዘብ ኪሳራ እንደደረሰበት ገልጿል።
በሌላ በኩል ጀንቦሮ ሪል እስቴት ባቀረበው መከላከያ፣ ክሱ የሕግ መሠረት የሌለው ነዉ ሲል ተከራክሯል። ድርጅቱ አክሎም "ጀንቦሮ" የሚለው ስም በጉራጌ ዞን የሚገኝ የመንደር ስም እንጂ ከሱዋሂሊው "ጃምቦ" ጋር ምንም ዓይነት የቋንቋ ዝምድና እንደሌለው ገልጿል።
የሪል እስቴት ደንበኞች ከፍተኛ ገንዘብ አውጥተው ከመግዛታቸው በፊት የድርጅቱን ማንነትና ታሪክ በሚገባ የሚመረምሩ በመሆናቸው፣ በስም ተመሳሳይነት ብቻ ይሳሳታሉ የሚለው ክስ ተቀባይነት የለውም ሲልም ጀንቦሮ ተከራክሯል።
seledadotio
seledadotio
በኢትዮጵያ የኮንስትራክሽንና የሪል እስቴት ኢንዱስትሪ ውስጥ ለሦስት አሥርተ ዓመታት ገደማ ስሙን የገነባው ጃምቦ ኮንስትራክሽን፣ አዲስ ወደ ገበያው በገባው ጀንቦሮ ሪል እስቴት ላይ የንግድ ምልክት ስያሜዬን ወስዶብኛል በሚል የ1 ሚሊዮን ብር የካሳ ክስ በፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት መሰረተ።
ጃምቦ ኮንስትራክሽን ለፍርድ ቤቱ ባቀረበው አቤቱታ፣ "ጀንቦሮ" የሚለው ስያሜ ከራሱ የንግድ ምልክት ጋር በድምፅ፣ በፊደላት አጻጻፍና በቃና ተመሳሳይነት ስላለው ደንበኞችንና ሚዲያን እያደናገረ ይገኛል ብሏል። ድርጅቱ ይህን ድርጊት "የብራንድ ነጠቃ" ሲል የገለጸው ሲሆን፣ በዚህም ምክንያት 1 ሚሊዮን ብር የሚገመት የገንዘብ ኪሳራ እንደደረሰበት ገልጿል።
በሌላ በኩል ጀንቦሮ ሪል እስቴት ባቀረበው መከላከያ፣ ክሱ የሕግ መሠረት የሌለው ነዉ ሲል ተከራክሯል። ድርጅቱ አክሎም "ጀንቦሮ" የሚለው ስም በጉራጌ ዞን የሚገኝ የመንደር ስም እንጂ ከሱዋሂሊው "ጃምቦ" ጋር ምንም ዓይነት የቋንቋ ዝምድና እንደሌለው ገልጿል።
የሪል እስቴት ደንበኞች ከፍተኛ ገንዘብ አውጥተው ከመግዛታቸው በፊት የድርጅቱን ማንነትና ታሪክ በሚገባ የሚመረምሩ በመሆናቸው፣ በስም ተመሳሳይነት ብቻ ይሳሳታሉ የሚለው ክስ ተቀባይነት የለውም ሲልም ጀንቦሮ ተከራክሯል።
seledadotio
seledadotio
3 months ago
ብራንዴ ተሰርቋል!
#ethiopia | በኢትዮጵያ የኮንስትራክሽንና የሪል እስቴት ዘርፍ ውስጥ የታወቀው ጃምቦ ኮንስትራክሽን፣ "ብራንዴ ተሰርቋል" በሚል በጀንቦሮ ሪል እስቴት ላይ የ1 ሚሊዮን ብር ክስ መመስረቱን የካፒታል ጋዜጣ ዘገባ ያመለክታል።
የክሱ ዝርዝር ነጥቦች እንደሚከተለው ቀርበዋል፡-
የጃምቦ ኮንስትራክሽን ክስ አቀራረብ
* የንግድ ምልክት ነጠቃ፦
ጃምቦ ኮንስትራክሽን ለሦስት አስርት ዓመታት ገደማ የገነባሁትን ስም አዲስ ወደ ገበያ የገባው ጀንቦሮ ሪል እስቴት ወስዶብኛል ሲል ከሷል።
* የስም ተመሳሳይነት፦
"ጀንቦሮ" የሚለው ስያሜ ከ"ጃምቦ" ጋር በድምፅ፣ በፊደላት አጻጻፍና በቃና ተመሳሳይነት ስላለው ደንበኞችንና ሚዲያን እያደናገረ ይገኛል ብሏል።
* የካሳ ጥያቄ፦
በዚህ የብራንድ ነጠቃ ምክንያት 1 ሚሊዮን ብር የሚገመት የገንዘብ ኪሳራ ደርሶብኛል በሚል ካሳ ጠይቋል።
የጀንቦሮ ሪል እስቴት መከላከያ
* የሕግ መሠረት፦
የቀረበው ክስ የሕግ መሠረት የሌለው ነው ሲል ጀንቦሮ ተከራክሯል።
* የስሙ አመጣጥ፦
"ጀንቦሮ" የሚለው ስም በጉራጌ ዞን የሚገኝ የመንደር ስም እንጂ ከሱዋሂሊው "ጃምቦ" ጋር ምንም ዓይነት የቋንቋ ዝምድና የለውም ብሏል።
* የደንበኞች ግንዛቤ፦
የሪል እስቴት ደንበኞች ከፍተኛ ገንዘብ አውጥተው ከመግዛታቸው በፊት የድርጅቱን ማንነትና ታሪክ በሚገባ የሚመረምሩ በመሆናቸው፣ በስም ተመሳሳይነት ብቻ ይሳሳታሉ የሚለው ክስ ተቀባይነት የለውም ሲል መከላከያውን አቅርቧል።
ጉዳዩ በአሁኑ ወቅት በፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት በመታየት ላይ ይገኛል።
#ጃምቦኮንስትራክሽን #ጀንቦሮሪልእስቴት #የንግድምልክት #ክስ #ኢትዮጵያ #jamboconstruction #jenbororealestate #ethiopia #trademarklaw #getutemesgen
#ethiopia | በኢትዮጵያ የኮንስትራክሽንና የሪል እስቴት ዘርፍ ውስጥ የታወቀው ጃምቦ ኮንስትራክሽን፣ "ብራንዴ ተሰርቋል" በሚል በጀንቦሮ ሪል እስቴት ላይ የ1 ሚሊዮን ብር ክስ መመስረቱን የካፒታል ጋዜጣ ዘገባ ያመለክታል።
የክሱ ዝርዝር ነጥቦች እንደሚከተለው ቀርበዋል፡-
የጃምቦ ኮንስትራክሽን ክስ አቀራረብ
* የንግድ ምልክት ነጠቃ፦
ጃምቦ ኮንስትራክሽን ለሦስት አስርት ዓመታት ገደማ የገነባሁትን ስም አዲስ ወደ ገበያ የገባው ጀንቦሮ ሪል እስቴት ወስዶብኛል ሲል ከሷል።
* የስም ተመሳሳይነት፦
"ጀንቦሮ" የሚለው ስያሜ ከ"ጃምቦ" ጋር በድምፅ፣ በፊደላት አጻጻፍና በቃና ተመሳሳይነት ስላለው ደንበኞችንና ሚዲያን እያደናገረ ይገኛል ብሏል።
* የካሳ ጥያቄ፦
በዚህ የብራንድ ነጠቃ ምክንያት 1 ሚሊዮን ብር የሚገመት የገንዘብ ኪሳራ ደርሶብኛል በሚል ካሳ ጠይቋል።
የጀንቦሮ ሪል እስቴት መከላከያ
* የሕግ መሠረት፦
የቀረበው ክስ የሕግ መሠረት የሌለው ነው ሲል ጀንቦሮ ተከራክሯል።
* የስሙ አመጣጥ፦
"ጀንቦሮ" የሚለው ስም በጉራጌ ዞን የሚገኝ የመንደር ስም እንጂ ከሱዋሂሊው "ጃምቦ" ጋር ምንም ዓይነት የቋንቋ ዝምድና የለውም ብሏል።
* የደንበኞች ግንዛቤ፦
የሪል እስቴት ደንበኞች ከፍተኛ ገንዘብ አውጥተው ከመግዛታቸው በፊት የድርጅቱን ማንነትና ታሪክ በሚገባ የሚመረምሩ በመሆናቸው፣ በስም ተመሳሳይነት ብቻ ይሳሳታሉ የሚለው ክስ ተቀባይነት የለውም ሲል መከላከያውን አቅርቧል።
ጉዳዩ በአሁኑ ወቅት በፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት በመታየት ላይ ይገኛል።
#ጃምቦኮንስትራክሽን #ጀንቦሮሪልእስቴት #የንግድምልክት #ክስ #ኢትዮጵያ #jamboconstruction #jenbororealestate #ethiopia #trademarklaw #getutemesgen
3 months ago
“ብራንዴ ተሰርቋል” በሚል ጃምቦ ኮንስትራክሽን በጀንቦሮ ሪል እስቴት ላይ የ1 ሚሊዮን ብር ክስ መሰረተ
በኢትዮጵያ የኮንስትራክሽንና የሪል እስቴት ኢንዱስትሪ ውስጥ ለሦስት አሥርተ ዓመታት ገደማ ስሙን የገነባው ጃምቦ ኮንስትራክሽን፣ አዲስ ወደ ገበያው በገባው ጀንቦሮ ሪል እስቴት ላይ የንግድ ምልክት ስያሜዬን ወስዶብኛል በሚል የ1 ሚሊዮን ብር የካሳ ክስ በፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት መሰረተ።
ጃምቦ ኮንስትራክሽን ለፍርድ ቤቱ ባቀረበው አቤቱታ፣ "ጀንቦሮ" የሚለው ስያሜ ከራሱ የንግድ ምልክት ጋር በድምፅ፣ በፊደላት አጻጻፍና በቃና ተመሳሳይነት ስላለው ደንበኞችንና ሚዲያን እያደናገረ ይገኛል ብሏል። ድርጅቱ ይህን ድርጊት "የብራንድ ነጠቃ" ሲል የገለጸው ሲሆን፣ በዚህም ምክንያት 1 ሚሊዮን ብር የሚገመት የገንዘብ ኪሳራ እንደደረሰበት ገልጿል።
በሌላ በኩል ጀንቦሮ ሪል እስቴት ባቀረበው መከላከያ፣ ክሱ የሕግ መሠረት የሌለው ነዉ ሲል ተከራክሯል። ድርጅቱ አክሎም "ጀንቦሮ" የሚለው ስም በጉራጌ ዞን የሚገኝ የመንደር ስም እንጂ ከሱዋሂሊው "ጃምቦ" ጋር ምንም ዓይነት የቋንቋ ዝምድና እንደሌለው ገልጿል።
የሪል እስቴት ደንበኞች ከፍተኛ ገንዘብ አውጥተው ከመግዛታቸው በፊት የድርጅቱን ማንነትና ታሪክ በሚገባ የሚመረምሩ በመሆናቸው፣ በስም ተመሳሳይነት ብቻ ይሳሳታሉ የሚለው ክስ ተቀባይነት የለውም ሲልም ጀንቦሮ ተከራክሯል።
ዝርዝሩን ያንብቡ
https://capitalethiopia.co...
በኢትዮጵያ የኮንስትራክሽንና የሪል እስቴት ኢንዱስትሪ ውስጥ ለሦስት አሥርተ ዓመታት ገደማ ስሙን የገነባው ጃምቦ ኮንስትራክሽን፣ አዲስ ወደ ገበያው በገባው ጀንቦሮ ሪል እስቴት ላይ የንግድ ምልክት ስያሜዬን ወስዶብኛል በሚል የ1 ሚሊዮን ብር የካሳ ክስ በፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት መሰረተ።
ጃምቦ ኮንስትራክሽን ለፍርድ ቤቱ ባቀረበው አቤቱታ፣ "ጀንቦሮ" የሚለው ስያሜ ከራሱ የንግድ ምልክት ጋር በድምፅ፣ በፊደላት አጻጻፍና በቃና ተመሳሳይነት ስላለው ደንበኞችንና ሚዲያን እያደናገረ ይገኛል ብሏል። ድርጅቱ ይህን ድርጊት "የብራንድ ነጠቃ" ሲል የገለጸው ሲሆን፣ በዚህም ምክንያት 1 ሚሊዮን ብር የሚገመት የገንዘብ ኪሳራ እንደደረሰበት ገልጿል።
በሌላ በኩል ጀንቦሮ ሪል እስቴት ባቀረበው መከላከያ፣ ክሱ የሕግ መሠረት የሌለው ነዉ ሲል ተከራክሯል። ድርጅቱ አክሎም "ጀንቦሮ" የሚለው ስም በጉራጌ ዞን የሚገኝ የመንደር ስም እንጂ ከሱዋሂሊው "ጃምቦ" ጋር ምንም ዓይነት የቋንቋ ዝምድና እንደሌለው ገልጿል።
የሪል እስቴት ደንበኞች ከፍተኛ ገንዘብ አውጥተው ከመግዛታቸው በፊት የድርጅቱን ማንነትና ታሪክ በሚገባ የሚመረምሩ በመሆናቸው፣ በስም ተመሳሳይነት ብቻ ይሳሳታሉ የሚለው ክስ ተቀባይነት የለውም ሲልም ጀንቦሮ ተከራክሯል።
ዝርዝሩን ያንብቡ
https://capitalethiopia.co...
Sponsored by
Surafel
3 months ago
የታሪካዊው የአድዋ የክተት ዓዋጅ መፈተሻ ጥያቄዎች
ጥያቄ 1፦ ዳግማዊ አፄ ሚኒሊክ የታሪካዊውን የክተት ዓዋጅ ያወጁት መቼ ነበር?
ሀ) መስከረም 17 ቀን 1887 ዓ.ም
ለ) መስከረም 17 ቀን 1888 ዓ.ም
ሐ) ጥቅምት 17 ቀን 1888 ዓ.ም
መ) የካቲት 23 ቀን 1888 ዓ.ም
ጥያቄ 2፦ በክተት ዓዋጁ መሠረት፣ አፄ ሚኒሊክ "ወደፊትም ያሳፍረኛል ብዬ አልጠራጠርም" በማለት ጽኑ እምነታቸውን የገለጹት በማን ላይ ነበር?
ሀ) በጦር መሪዎቻቸው ብቃት
ለ) በዘመናዊ የጦር መሣሪያዎች
ሐ) በእግዚአብሔር ረዳትነት
መ) በሠራዊቱ ብዛት
ጥያቄ 3፦ በራስ መኮንን ወልደሚካኤል መሪነት አስቀድሞ ወደ ጦር ግንባር የዘመተው የትኛው ጦር ነው?
ሀ) የጎጃም ጦር
ለ) የትግራይ ጦር
ሐ) የሐረር ጦር
መ) የጉራጌና ጨቦ ጦር
ጥያቄ 4፦ በአድዋ ጦርነት ወቅት የጉራጌና የጨቦን ጦር የመሩት ታዋቂ የጦር መሪ ማን ነበሩ?
ሀ) ራስ ቢትወደድ መንገሻ
ለ) ፊታውራሪ ሀብተ ጊዮርጊስ
ሐ) ደጃዝማች ወልዴ አሻግሬ
መ) ንጉሥ ተክለሃይማኖት
ጥያቄ 5፦ አብዛኛው የደቡብ፣ የምስራቅ፣ የምዕራብና የመካከለኛው ኢትዮጵያ ጦር ንጉሠ ነገሥቱን ተከትሎ የከተመበት (የሰፈረበት) ቦታ የት ነው?
ሀ) አሽንጌ ሐይቅ
ለ) ደጋ ሐሙስ
ሐ) መቀሌ
መ) ወረኢሉ
መልሳቹን ኮመንት ላይ አስቀምጡልን 👇
ጥያቄ 1፦ ዳግማዊ አፄ ሚኒሊክ የታሪካዊውን የክተት ዓዋጅ ያወጁት መቼ ነበር?
ሀ) መስከረም 17 ቀን 1887 ዓ.ም
ለ) መስከረም 17 ቀን 1888 ዓ.ም
ሐ) ጥቅምት 17 ቀን 1888 ዓ.ም
መ) የካቲት 23 ቀን 1888 ዓ.ም
ጥያቄ 2፦ በክተት ዓዋጁ መሠረት፣ አፄ ሚኒሊክ "ወደፊትም ያሳፍረኛል ብዬ አልጠራጠርም" በማለት ጽኑ እምነታቸውን የገለጹት በማን ላይ ነበር?
ሀ) በጦር መሪዎቻቸው ብቃት
ለ) በዘመናዊ የጦር መሣሪያዎች
ሐ) በእግዚአብሔር ረዳትነት
መ) በሠራዊቱ ብዛት
ጥያቄ 3፦ በራስ መኮንን ወልደሚካኤል መሪነት አስቀድሞ ወደ ጦር ግንባር የዘመተው የትኛው ጦር ነው?
ሀ) የጎጃም ጦር
ለ) የትግራይ ጦር
ሐ) የሐረር ጦር
መ) የጉራጌና ጨቦ ጦር
ጥያቄ 4፦ በአድዋ ጦርነት ወቅት የጉራጌና የጨቦን ጦር የመሩት ታዋቂ የጦር መሪ ማን ነበሩ?
ሀ) ራስ ቢትወደድ መንገሻ
ለ) ፊታውራሪ ሀብተ ጊዮርጊስ
ሐ) ደጃዝማች ወልዴ አሻግሬ
መ) ንጉሥ ተክለሃይማኖት
ጥያቄ 5፦ አብዛኛው የደቡብ፣ የምስራቅ፣ የምዕራብና የመካከለኛው ኢትዮጵያ ጦር ንጉሠ ነገሥቱን ተከትሎ የከተመበት (የሰፈረበት) ቦታ የት ነው?
ሀ) አሽንጌ ሐይቅ
ለ) ደጋ ሐሙስ
ሐ) መቀሌ
መ) ወረኢሉ
መልሳቹን ኮመንት ላይ አስቀምጡልን 👇
3 months ago
ከቤተ መንግስት ዘበኝነት እስከ አድዋ ድል የጥበብ ማማ ፡ ፊታውራሪ ሀብተ ጊዮርጊስ (አባ መላ)
ይህ ታሪክ ስለ አንድ ተራ ሰው አይደለም፤ ይህ ታሪክ ስለ አንዲት ሀገር ትንሳኤ፣ ስለ አንድ ምርኮኛ ጀግንነት እና ስለ አንዲት ነፍስ ፍጹም ታማኝነት የሚተርክ የኢትዮጵያዊነት ማህተም ያለው ዛሬ አድዋ ድልን ስናከብር በፍፁም የማንረሳው ለወደፊትም የምንዘክረው ሰው ታሪክ ነው።
ላለፉት 130 አመታት እንዲሁም ዛሬም ድረስ በአድዋ ተራሮች ላይ የሚስተጋባው የድል ዝማሬ የፊታውራሪ ሀብተ ጊዮርጊስ ዲነግዴ የጥበብና የደም ውጤት አለበት። ይህን በኩራት እንናገራለን።
በ1840ዎቹ አጋማሽ በደቡብ ሸዋ ጨቦ ምድር ወጣቱ ሀብተ ጊዮርጊስ በጦርነት ተማርኮ ወደ አፄ ምኒልክ ግቢ ሲመጣ፣ እግሩ ላይ የነበረው ሰንሰለት እንጂ ልቡ ውስጥ ያለው እሳት አልታየም ነበር።
ምርኮኛ ሆኖ የገባው ወጣት፣ በቤተመንግስት ዘበኝነት ተመደበ።
አንድ ምሽት አፄ ምኒልክ በቤተመንግስቱ ቅጥር ግቢ ሲዘዋወሩ፣ ይህ ወጣት ዘበኛ በብርድ እየተገረፈ ግን ደግሞ እንደ ቋጥኝ ጸንቶ በንቃት ሲጠብቅ አዩት። ንጉሡ ቀርበው "አንተ ልጅ፣ አይበርድህም ወይ?" ሲሉ ጠየቁት። ወጣቱም ቀና ብሎ "የንጉሡ ትዕዛዝ ከብርዱ በላይ ያሞቀኛል" ብሎ መለሰ።
ምኒልክ በዚያች ቅጽበት በወጣቱ አይን ውስጥ የታማኝነትን ጥልቅ ባህር አዩ። ከዚያ ቀን ጀምሮ ሀብተ ጊዮርጊስ ከዘበኝነት ወደ ቅርብ አሽከርነት፣ ከቅርብ አሽከርነት ወደ መላተኛ መካሪነት ተሸጋገረ።
ባለማወቅ እና በትዕቢት ጣልያን 1888 ዓ.ም ኢትዮጵያ ለመግዛት መጣች። በዚህም ኢትዮጵያ በታሪኳ ታይቶ የማይታወቅ የህልውና አደጋ ተደቀነባት። የጣሊያን ጦር ዘመናዊ መሣሪያ ታጥቆ፣ የአፍሪካን ኩራት ለመቅበር ወደ አድዋ መጣ። በዚህ ጊዜ ነበር ሀብተ ጊዮርጊስ "አባ መላ" የሚለውን ስም በታሪክ መዝገብ ላይ በደማቅ ቀለም የጻፉት።
አባ መላ ከመቶ ሺህ በላይ የሚሆን ሰራዊት፣ አዝማቾችና ፈረሶች ከሸዋ እስከ አድዋ ሲጓዙ ሳይራቡና ሳይጠሙ እንዲደርሱ ማድረግ ከጦርነቱ በላይ ከባድ ነበር። ሀብተ ጊዮርጊስ ግን በየመንገዱ ስንቅ የሚያከማቹ "ጎተራዎችን" በማዘጋጀት፣ ሰራዊቱ በረሃብ ተዳክሞ ለጠላት እጅ እንዳይሰጥ አደረጉ።
ይህ ብርቱ ሰው ጣሊያኖች የኢትዮጵያን ሰራዊት ቁጥርና አቅጣጫ ለማወቅ ደፋ ቀና ሲሉ አባ መላ ግን የራሳቸውን ሰላዮች ወደ ጣሊያን ምሽግ በመላክ፣ የሀሰት መረጃ እንዲደርሳቸው አደረጉ። ጣሊያኖች "የኢትዮጵያ ጦር ተራርቋል፣ ተጣልቷል፣ ስንቅ አልቆበታል" የሚል የሀሰት መረጃ እንዲያምኑ በማድረግ ወደ ወጥመዱ እንዲገቡ መሯቸው።
በዚህም አላበቁም ጦርነቱ ሲለኮስ ሀብተ ጊዮርጊስ በስተጀርባ የሚመክሩ ብቻ አልነበሩም። "ፊታውራሪ" ማለት የጦር ግንባር ቀደም መሪ ማለት ነው። ጥይት እንደ በረዶ በሚዘንብበት፣ መድፍ ምድሩን በሚያናውጥበት በዚያ አስፈሪ ሰዓት፣ ሀብተ ጊዮርጊስ በፈረሳቸው ላይ ሆነው "ለሀገራችሁ! ለክብራችሁ!" እያሉ ሰራዊቱን በመምራት የጠላትን ምሽግ ሰባበሩ።
በአድዋ ድል ኢትዮጵያ ተቀዳጀች። ኢትዮጵያ በዓለም አደባባይ ከፍ አለች። ሀብተ ጊዮርጊስም የኢትዮጵያ የመጀመሪያው የጦር ሚኒስትር ሆኑ።
ከታሪካቸው መሀል እጅግ ልብ የሚነካ የሚሆነው ከአፄ ምኒልክ ጋር የነበራቸው ቁርኝት ነው።
አፄ ምኒልክ በታመሙበትና አልጋ ላይ በዋሉበት አስቸጋሪ ወቅት፣ ቤተመንግስቱ በሴራና በፖለቲካ ትኩሳት ሲናጥ፣ ሀብተ ጊዮርጊስ እንደ አጥንት ለምኒልክ ጸኑ። ንጉሡ መናገር ባቃታቸው ጊዜ እንኳን፣ የሀብተ ጊዮርጊስን እጅ ይዘው አይን አይናቸውን እያዩ ይጽናኑ ነበር።
ታኅሣሥ 3 ቀን 1906 ዓ.ም. ታላቁ ንጉሥ አፄ ምኒልክ አረፉ። ሀብተ ጊዮርጊስ ስቅስቅ ብለው አለቀሱ፣ ግን አልደከሙም። "ንጉሡ ቢሞቱም ሀገር መሞት የለባትም" ብለው ለ13 ዓመታት ኢትዮጵያን ጠበቁ። ንግሥት ዘውዲቱና አልጋ ወራሽ ተፈሪ መኮንን (ኃይለ ሥላሴ) በሰላም ሀገሪቱን እንዲመሩ የጀርባ አጥንት ሆኑ።
ታኅሣሥ 3 ቀን 1919 ዓ.ም.። አፄ ምኒልክ ካረፉ ልክ በ13ኛው ዓመት፣ በዚያችው ቀንና በዚያችው ሰዓት ፊታውራሪ ሀብተ ጊዮርጊስም አረፉ። ይህ የአጋጣሚ ጉዳይ ሳይሆን፣ የፍጹም ታማኝነት መንፈሳዊ ትስስር እንደሆነ የታሪክ ጸሐፊዎች ይገልጻሉ።
በቀብራቸው ቀን በአዲስ አበባ ታይቶ የማይታወቅ የልቅሶ ድምፅ ተሰማ። የጦር ሰራዊቱ፣ ድሆች፣ እናቶችና ህፃናት "አባ መላ ወዴት ሄዱ?" እያሉ ምድሩን በእንባቸው አጠቡት።
ባለቤታቸው ወይዘሮ አልታየ ወርቅ፣ የባላቸውን ራስ ወርቅና የክብር ልብስ ይዘው በሀዘን ሲንሰቀሰቁ፣ የኢትዮጵያ ትልቅ ተራራ የተናደ መሰለ።
ታላቁ የቅኔ አዋቂ ተሰማ እሸቴ እንዲህ ብሎ ተቀኘ፦
"ከምኒልክ ይዞ እስካሁን ድረስ፣
የአልታየ ሞት ሆነ የሀብተ ጊዮርጊስ።"
(ትርጉሙ፡- ሀብተ ጊዮርጊስ ምኒልክ ከሞቱበት ቀን ጀምሮ እስከ ዛሬ ድረስ በቁም ሞተው ነበር፤ ዛሬ ግን ያ የታየው ሞታቸው እውነት ሆነ።)
ማንነትና መነሻ ስኬትን አይወስነውም። ታማኝነትና ብልህነት ካለ፣ ከዝቅተኛው ስፍራ ተነስተን የሀገር መሪ መሆን እንደምንችል አባ መላ ትልቅ ምስክር ናቸው።
በ"አባ መላ" ጥበብ ጦርነትና ግጭት ሁልጊዜ በጉልበት አይፈታም የሚል ፍልስፍና ተምረናል። ብልሃትና ማስተዋል ለአባ መላ ከሺህ መድፎች በላይ ኃይል ነበራቸው።
ሀብተ ጊዮርጊስ የኦሮሞና የጉራጌ ደም ቢኖራቸውም፣ ህይወታቸውን የሰጡት ግን ለኢትዮጵያ አንድነት ነው። ዘር ሳይለዩ፣ ሃይማኖት ሳይከፍሉ ለጥቁር ህዝብ ነፃነት ቆሙ።
ዛሬ በአዲስ አበባ "ሀብተ ጊዮርጊስ ድልድይ" ላይ ስትቆም፣ ያ ድልድይ በድንጋይ ብቻ የተገነባ እንዳይመስልህ። ያ ድልድይ የተገነባው በአባ መላ አጥንት፣ በደምና በጽኑ ታማኝነት ላይ ነው።
ፊታውራሪ ሀብተ ጊዮርጊስ ዲነግዴ፤ አንተ የጥበብ ማማ፣ አንተ የታማኝነት መዝገብ፣ አንተ የአድዋ ድል ቀኝ እጅ! ስምህ ለዘላለም በኢትዮጵያውያን ልብ ውስጥ ህያው ሆኖ ይኖራል።
ይህ ታሪክ ስለ አንድ ተራ ሰው አይደለም፤ ይህ ታሪክ ስለ አንዲት ሀገር ትንሳኤ፣ ስለ አንድ ምርኮኛ ጀግንነት እና ስለ አንዲት ነፍስ ፍጹም ታማኝነት የሚተርክ የኢትዮጵያዊነት ማህተም ያለው ዛሬ አድዋ ድልን ስናከብር በፍፁም የማንረሳው ለወደፊትም የምንዘክረው ሰው ታሪክ ነው።
ላለፉት 130 አመታት እንዲሁም ዛሬም ድረስ በአድዋ ተራሮች ላይ የሚስተጋባው የድል ዝማሬ የፊታውራሪ ሀብተ ጊዮርጊስ ዲነግዴ የጥበብና የደም ውጤት አለበት። ይህን በኩራት እንናገራለን።
በ1840ዎቹ አጋማሽ በደቡብ ሸዋ ጨቦ ምድር ወጣቱ ሀብተ ጊዮርጊስ በጦርነት ተማርኮ ወደ አፄ ምኒልክ ግቢ ሲመጣ፣ እግሩ ላይ የነበረው ሰንሰለት እንጂ ልቡ ውስጥ ያለው እሳት አልታየም ነበር።
ምርኮኛ ሆኖ የገባው ወጣት፣ በቤተመንግስት ዘበኝነት ተመደበ።
አንድ ምሽት አፄ ምኒልክ በቤተመንግስቱ ቅጥር ግቢ ሲዘዋወሩ፣ ይህ ወጣት ዘበኛ በብርድ እየተገረፈ ግን ደግሞ እንደ ቋጥኝ ጸንቶ በንቃት ሲጠብቅ አዩት። ንጉሡ ቀርበው "አንተ ልጅ፣ አይበርድህም ወይ?" ሲሉ ጠየቁት። ወጣቱም ቀና ብሎ "የንጉሡ ትዕዛዝ ከብርዱ በላይ ያሞቀኛል" ብሎ መለሰ።
ምኒልክ በዚያች ቅጽበት በወጣቱ አይን ውስጥ የታማኝነትን ጥልቅ ባህር አዩ። ከዚያ ቀን ጀምሮ ሀብተ ጊዮርጊስ ከዘበኝነት ወደ ቅርብ አሽከርነት፣ ከቅርብ አሽከርነት ወደ መላተኛ መካሪነት ተሸጋገረ።
ባለማወቅ እና በትዕቢት ጣልያን 1888 ዓ.ም ኢትዮጵያ ለመግዛት መጣች። በዚህም ኢትዮጵያ በታሪኳ ታይቶ የማይታወቅ የህልውና አደጋ ተደቀነባት። የጣሊያን ጦር ዘመናዊ መሣሪያ ታጥቆ፣ የአፍሪካን ኩራት ለመቅበር ወደ አድዋ መጣ። በዚህ ጊዜ ነበር ሀብተ ጊዮርጊስ "አባ መላ" የሚለውን ስም በታሪክ መዝገብ ላይ በደማቅ ቀለም የጻፉት።
አባ መላ ከመቶ ሺህ በላይ የሚሆን ሰራዊት፣ አዝማቾችና ፈረሶች ከሸዋ እስከ አድዋ ሲጓዙ ሳይራቡና ሳይጠሙ እንዲደርሱ ማድረግ ከጦርነቱ በላይ ከባድ ነበር። ሀብተ ጊዮርጊስ ግን በየመንገዱ ስንቅ የሚያከማቹ "ጎተራዎችን" በማዘጋጀት፣ ሰራዊቱ በረሃብ ተዳክሞ ለጠላት እጅ እንዳይሰጥ አደረጉ።
ይህ ብርቱ ሰው ጣሊያኖች የኢትዮጵያን ሰራዊት ቁጥርና አቅጣጫ ለማወቅ ደፋ ቀና ሲሉ አባ መላ ግን የራሳቸውን ሰላዮች ወደ ጣሊያን ምሽግ በመላክ፣ የሀሰት መረጃ እንዲደርሳቸው አደረጉ። ጣሊያኖች "የኢትዮጵያ ጦር ተራርቋል፣ ተጣልቷል፣ ስንቅ አልቆበታል" የሚል የሀሰት መረጃ እንዲያምኑ በማድረግ ወደ ወጥመዱ እንዲገቡ መሯቸው።
በዚህም አላበቁም ጦርነቱ ሲለኮስ ሀብተ ጊዮርጊስ በስተጀርባ የሚመክሩ ብቻ አልነበሩም። "ፊታውራሪ" ማለት የጦር ግንባር ቀደም መሪ ማለት ነው። ጥይት እንደ በረዶ በሚዘንብበት፣ መድፍ ምድሩን በሚያናውጥበት በዚያ አስፈሪ ሰዓት፣ ሀብተ ጊዮርጊስ በፈረሳቸው ላይ ሆነው "ለሀገራችሁ! ለክብራችሁ!" እያሉ ሰራዊቱን በመምራት የጠላትን ምሽግ ሰባበሩ።
በአድዋ ድል ኢትዮጵያ ተቀዳጀች። ኢትዮጵያ በዓለም አደባባይ ከፍ አለች። ሀብተ ጊዮርጊስም የኢትዮጵያ የመጀመሪያው የጦር ሚኒስትር ሆኑ።
ከታሪካቸው መሀል እጅግ ልብ የሚነካ የሚሆነው ከአፄ ምኒልክ ጋር የነበራቸው ቁርኝት ነው።
አፄ ምኒልክ በታመሙበትና አልጋ ላይ በዋሉበት አስቸጋሪ ወቅት፣ ቤተመንግስቱ በሴራና በፖለቲካ ትኩሳት ሲናጥ፣ ሀብተ ጊዮርጊስ እንደ አጥንት ለምኒልክ ጸኑ። ንጉሡ መናገር ባቃታቸው ጊዜ እንኳን፣ የሀብተ ጊዮርጊስን እጅ ይዘው አይን አይናቸውን እያዩ ይጽናኑ ነበር።
ታኅሣሥ 3 ቀን 1906 ዓ.ም. ታላቁ ንጉሥ አፄ ምኒልክ አረፉ። ሀብተ ጊዮርጊስ ስቅስቅ ብለው አለቀሱ፣ ግን አልደከሙም። "ንጉሡ ቢሞቱም ሀገር መሞት የለባትም" ብለው ለ13 ዓመታት ኢትዮጵያን ጠበቁ። ንግሥት ዘውዲቱና አልጋ ወራሽ ተፈሪ መኮንን (ኃይለ ሥላሴ) በሰላም ሀገሪቱን እንዲመሩ የጀርባ አጥንት ሆኑ።
ታኅሣሥ 3 ቀን 1919 ዓ.ም.። አፄ ምኒልክ ካረፉ ልክ በ13ኛው ዓመት፣ በዚያችው ቀንና በዚያችው ሰዓት ፊታውራሪ ሀብተ ጊዮርጊስም አረፉ። ይህ የአጋጣሚ ጉዳይ ሳይሆን፣ የፍጹም ታማኝነት መንፈሳዊ ትስስር እንደሆነ የታሪክ ጸሐፊዎች ይገልጻሉ።
በቀብራቸው ቀን በአዲስ አበባ ታይቶ የማይታወቅ የልቅሶ ድምፅ ተሰማ። የጦር ሰራዊቱ፣ ድሆች፣ እናቶችና ህፃናት "አባ መላ ወዴት ሄዱ?" እያሉ ምድሩን በእንባቸው አጠቡት።
ባለቤታቸው ወይዘሮ አልታየ ወርቅ፣ የባላቸውን ራስ ወርቅና የክብር ልብስ ይዘው በሀዘን ሲንሰቀሰቁ፣ የኢትዮጵያ ትልቅ ተራራ የተናደ መሰለ።
ታላቁ የቅኔ አዋቂ ተሰማ እሸቴ እንዲህ ብሎ ተቀኘ፦
"ከምኒልክ ይዞ እስካሁን ድረስ፣
የአልታየ ሞት ሆነ የሀብተ ጊዮርጊስ።"
(ትርጉሙ፡- ሀብተ ጊዮርጊስ ምኒልክ ከሞቱበት ቀን ጀምሮ እስከ ዛሬ ድረስ በቁም ሞተው ነበር፤ ዛሬ ግን ያ የታየው ሞታቸው እውነት ሆነ።)
ማንነትና መነሻ ስኬትን አይወስነውም። ታማኝነትና ብልህነት ካለ፣ ከዝቅተኛው ስፍራ ተነስተን የሀገር መሪ መሆን እንደምንችል አባ መላ ትልቅ ምስክር ናቸው።
በ"አባ መላ" ጥበብ ጦርነትና ግጭት ሁልጊዜ በጉልበት አይፈታም የሚል ፍልስፍና ተምረናል። ብልሃትና ማስተዋል ለአባ መላ ከሺህ መድፎች በላይ ኃይል ነበራቸው።
ሀብተ ጊዮርጊስ የኦሮሞና የጉራጌ ደም ቢኖራቸውም፣ ህይወታቸውን የሰጡት ግን ለኢትዮጵያ አንድነት ነው። ዘር ሳይለዩ፣ ሃይማኖት ሳይከፍሉ ለጥቁር ህዝብ ነፃነት ቆሙ።
ዛሬ በአዲስ አበባ "ሀብተ ጊዮርጊስ ድልድይ" ላይ ስትቆም፣ ያ ድልድይ በድንጋይ ብቻ የተገነባ እንዳይመስልህ። ያ ድልድይ የተገነባው በአባ መላ አጥንት፣ በደምና በጽኑ ታማኝነት ላይ ነው።
ፊታውራሪ ሀብተ ጊዮርጊስ ዲነግዴ፤ አንተ የጥበብ ማማ፣ አንተ የታማኝነት መዝገብ፣ አንተ የአድዋ ድል ቀኝ እጅ! ስምህ ለዘላለም በኢትዮጵያውያን ልብ ውስጥ ህያው ሆኖ ይኖራል።
4 months ago
አስቸኳይ የእርዳታ ጥሪ
አቶ ከለላ ሃይሌ በጉራጌ ዞን እምድብር ከተማ አስተዳደር 01 ቀበሌ መንደር የሰሜና ፉካ ነዋሪ ሲሆን በአሁን ሰዓት GBS INFECTIN በሚባል ህመም (ህመሙ ሙሉ የሠውነት አካል በመቆጣጠር ለማዘዝ በማይቻልበት ሁኔታ የሚያጠቃ ነው) በአዲስ አበባ ከተማ ላንሴት ሆስፒታል በህክምና እየተረዳ ይገኛል።
ከዚህ ህክምና ክትትል በተጨማሪና አስችኳይ የሆነ የነርቭ ህክም እንደሚያስፈልገው ተነግሮታል።
ለህክምናው አንድ ሚሊየን ገንዘብ በመጠየቁ የወንድማችንን ህይወት ለማዳን ቤተሰብ የተቻለውን ርብርብ በማድረግ ላይ ይገኛል።
ሆኖም ግን ህክምናው ከፍተኛ ገንዘብ እንደሚያስፈልገው በሀኪሞቹ ስለተነገረን በቤተሰብ አቅም የሚሸፈን ባለመሆኑ እናንተ ደጋግ ኢትዮጵያውያን ለወገን ደራሽ ወገን በመሆኑ የወንድማችንን ነፍስ ለመታደግ በሚከተሉት የባንክ አካውንቶች እንድታግዙን ስንል በፈጣሪ ስም ተማፅኖአችንን እናቀርባለን ።
የንግድ ባንክ አካውንት ፡
እንጦንዮስ ሀይሌ (ወንድም)
1000147028467
አቢሲኒያ ባንክ
219233531
ስልክ ቁጥር
እንጦንዮስ=0963280978
ዮናስ=0923503693
ማየት =0902368086
ከቤተሰቦቹ
አቶ ከለላ ሃይሌ በጉራጌ ዞን እምድብር ከተማ አስተዳደር 01 ቀበሌ መንደር የሰሜና ፉካ ነዋሪ ሲሆን በአሁን ሰዓት GBS INFECTIN በሚባል ህመም (ህመሙ ሙሉ የሠውነት አካል በመቆጣጠር ለማዘዝ በማይቻልበት ሁኔታ የሚያጠቃ ነው) በአዲስ አበባ ከተማ ላንሴት ሆስፒታል በህክምና እየተረዳ ይገኛል።
ከዚህ ህክምና ክትትል በተጨማሪና አስችኳይ የሆነ የነርቭ ህክም እንደሚያስፈልገው ተነግሮታል።
ለህክምናው አንድ ሚሊየን ገንዘብ በመጠየቁ የወንድማችንን ህይወት ለማዳን ቤተሰብ የተቻለውን ርብርብ በማድረግ ላይ ይገኛል።
ሆኖም ግን ህክምናው ከፍተኛ ገንዘብ እንደሚያስፈልገው በሀኪሞቹ ስለተነገረን በቤተሰብ አቅም የሚሸፈን ባለመሆኑ እናንተ ደጋግ ኢትዮጵያውያን ለወገን ደራሽ ወገን በመሆኑ የወንድማችንን ነፍስ ለመታደግ በሚከተሉት የባንክ አካውንቶች እንድታግዙን ስንል በፈጣሪ ስም ተማፅኖአችንን እናቀርባለን ።
የንግድ ባንክ አካውንት ፡
እንጦንዮስ ሀይሌ (ወንድም)
1000147028467
አቢሲኒያ ባንክ
219233531
ስልክ ቁጥር
እንጦንዮስ=0963280978
ዮናስ=0923503693
ማየት =0902368086
ከቤተሰቦቹ
4 months ago
😭 "ልጄን ሙባረክን አፋልጉኝ!" 🙏
#ethiopia | "በህመም ምክንያት ተለያየን... አሁን ከጠፋብኝ አመታት አለፉ... እባካችሁ አገናኙኝ" - እናት አማና አብዱ
ስሜ አማና አብዱ ሙሳ ይባላል። ልጄ ሙባረክ ከድር ኑሪ ይባላል። የተወለደው በ1994 ዓ.ም ሲሆን አሁን የ24 ዓመት ወጣት ነው።
የተለያየንበት ምክንያት:
በደቡብ ክልል፣ ጉራጌ ዞን፣ ጌታ ወረዳ፣ ቀቡል ቀበሌ፣ በዳዎ መንደር ከአባቱ አቶ ከድር ኑሪ ጋር በጋብቻ ስንኖር፤ በገጠመኝ ድንገተኛ ህመም ምክንያት ልጄን ገና በ5 ዓመቱ ለአባቱ እና ለአያቱ ትቼ ለህክምና ወደ አዲስ አበባ መጣሁ።
የጠፋበት ሁኔታ:
ልጄ ሙባረክ እስከ 7 ዓመቱ ከአያቱ ጋር ከኖረ በኋላ፤ አባቱ ወደ ናዝሬት (አዳማ) ወስዶት እስከ 13 ዓመቱ አብሮት ኖሯል። ነገር ግን በ13 ዓመቱ "ከቤተሰብ ባለመስማማቱ" በሚል ምክንያት እንደጠፋ ተነገረኝ። ከዚያ ጊዜ ጀምሮ እያፈላለግሁት ቢሆንም ላገኘው አልቻልኩም።
እባካችሁ ልጄን ሙባረክ ከድርን ያያችሁ ወይም ያለበትን የምታውቁ በፈጣሪ ስም እንድትጠቁሙኝ እለምናለሁ።
የእናት አንጀት አርሮ አይቀርምና ተባበሩኝ!
📞 ለማሳወቅ:
+251 919 17 82 87 (እናት አማና አብዱ
ሼር በማድረግ ለሌሎች እንዲደርስ እርዱኝ!
ፎቶግራፉ - የአባቱ ነው።
#missingperson #helpfindhim #mubarekkedir #guragezone #getawereda #nazret #adama #ethiopia #share #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን
#ethiopia | "በህመም ምክንያት ተለያየን... አሁን ከጠፋብኝ አመታት አለፉ... እባካችሁ አገናኙኝ" - እናት አማና አብዱ
ስሜ አማና አብዱ ሙሳ ይባላል። ልጄ ሙባረክ ከድር ኑሪ ይባላል። የተወለደው በ1994 ዓ.ም ሲሆን አሁን የ24 ዓመት ወጣት ነው።
የተለያየንበት ምክንያት:
በደቡብ ክልል፣ ጉራጌ ዞን፣ ጌታ ወረዳ፣ ቀቡል ቀበሌ፣ በዳዎ መንደር ከአባቱ አቶ ከድር ኑሪ ጋር በጋብቻ ስንኖር፤ በገጠመኝ ድንገተኛ ህመም ምክንያት ልጄን ገና በ5 ዓመቱ ለአባቱ እና ለአያቱ ትቼ ለህክምና ወደ አዲስ አበባ መጣሁ።
የጠፋበት ሁኔታ:
ልጄ ሙባረክ እስከ 7 ዓመቱ ከአያቱ ጋር ከኖረ በኋላ፤ አባቱ ወደ ናዝሬት (አዳማ) ወስዶት እስከ 13 ዓመቱ አብሮት ኖሯል። ነገር ግን በ13 ዓመቱ "ከቤተሰብ ባለመስማማቱ" በሚል ምክንያት እንደጠፋ ተነገረኝ። ከዚያ ጊዜ ጀምሮ እያፈላለግሁት ቢሆንም ላገኘው አልቻልኩም።
እባካችሁ ልጄን ሙባረክ ከድርን ያያችሁ ወይም ያለበትን የምታውቁ በፈጣሪ ስም እንድትጠቁሙኝ እለምናለሁ።
የእናት አንጀት አርሮ አይቀርምና ተባበሩኝ!
📞 ለማሳወቅ:
+251 919 17 82 87 (እናት አማና አብዱ
ሼር በማድረግ ለሌሎች እንዲደርስ እርዱኝ!
ፎቶግራፉ - የአባቱ ነው።
#missingperson #helpfindhim #mubarekkedir #guragezone #getawereda #nazret #adama #ethiopia #share #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን
4 months ago
#ethiopia | አጋዝ ገብረየሱስ ኃይለማሪያም ጉራጌ አቀፍ የምርምርና የድርሰር ስራዎች እንዲሁም ''የሚሊኒየሙ መሸኛና መቀበያ'' ፎቶግራፎችን ለብሔራዊ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት (ወመዘክር) በስጦታ አበረከቱ።
የደራሲ ገብረየሱስ ኃይለማርያም ከ28 ዓመት በፊት (በፈረንጆቹ ሚሊኒየም የመጨረሻው ለሊት እና ንጋት) ወደ ወጨጫ ተራራ በመጓዝ ያነሷቸው የሚሊኒየሙ ጀንበር መሸኛና መቀበያ ፎቶግራፎችን ጨምሮ የጫሙት ሽካ፣ ተኬትነት አጂነት/አገኪ፣ ነሁቸርና The Gurage and their Culture የተሰኙ የድርሰት ሥራዎቻቸውን ለብሔራዊ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት (ወመዘክር) አስረክበዋል።
ለጉራጌ በቋንቋ፣ በባህልና በማኅበረሰብ ልማት ዘርፎች ያበረከቷቸው የሕይወት ዘመን አገልግሎቶች "አጋዝ" የሚል ባህላዊ ስያሜ የተሰጣቸው አጋዝ ገብረኢየሱስ ኃይለማርያም በጉራግኛ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ 16 መጽሐፍትን ጽፈዋል።
ለጉራጌ ባህልና ቋንቋ ልማት ካበረከቱት አስተዋጽኦ ባሻገር የጉራጌ ባህል ማእከል እና የጉራጌ ሕዝብ ራስ አገዝ ልማት ድርጅትን (ጉህራልድ) በምስረታ ሂደት ላይ ላቅ ያለ ሚና ነበራቸው። በሌሎች ሀገራዊና ዓለምአቀፍ ተቋማትም አሻራቸውን አኑረዋል።
በዚሁ ወቅት የብሔራዊ ቤተመዛግብት እና ቤተ መፅሀፍት አገልግሎት ፅህፈት ቤት ኅላፊ አቶ አባተ ካሣው እንደተናገሩት ደራሲገብረየሱስ በኢትዮጵያ በብሔረሰቦች ቋንቋ ድርሰት መጽሐፍ ከጀመሩት ውስጥ ናቸው ያሉ ሲሆን ታሪካዊ ሰነዶችን ለወመዘከወር በማስረከባቸው የተሰማንን ልባዊ ደስታ እንገልፃለን ብለዋል።
ለደራሲ ገብረየሱስም ከወመዘክር የተዘጋጀ የእውቅናና ምስጋና የምስክር ወረቀት ሰርተፊኬት ሰጥተዋል።
በዝግጅቱ ላይ የተገኙት የጉራጌ ዞን ባህልና ቱሪዝም መምሪያ ኃላፊ ወይዘሮ መሠረት አመርጋ በበኩላቸው እንዲህ አይነት ታሪካዊ ስራዎች በሰነድነት ታስበው የርክክብ ሥነ ሥርዓቱ መዘጋጀቱ ለሀገር ትልቅ ነገር ነው ብለዋል።
ደራሲ አጋዝ ገብረየሱስ ሀይለማርያም በበኩላቸው ስራዎቹን ሳከናውን እዚህ ይደርሳል ብዬ ባይሆንም የበርካታ ታሪክና ባለታሪኮች ሰነድ መገኛ የሆነው ወመዘክ ፎቶግራፎቼንና የድርሰት ስራዎቼን በአሻራነት መሰነድ በመቻሉ ደስታ ተሰምቶኛል ብለዋል።
ዝግጅቱ ተወዳጅ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን ከሶዶ ለማ ሚድያ ጋር በመተባበር አዘጋጅተውታል።
ዓለም አቀፍ የጉራጌ ማህበር - International Gurage Association - IGA
የደራሲ ገብረየሱስ ኃይለማርያም ከ28 ዓመት በፊት (በፈረንጆቹ ሚሊኒየም የመጨረሻው ለሊት እና ንጋት) ወደ ወጨጫ ተራራ በመጓዝ ያነሷቸው የሚሊኒየሙ ጀንበር መሸኛና መቀበያ ፎቶግራፎችን ጨምሮ የጫሙት ሽካ፣ ተኬትነት አጂነት/አገኪ፣ ነሁቸርና The Gurage and their Culture የተሰኙ የድርሰት ሥራዎቻቸውን ለብሔራዊ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት (ወመዘክር) አስረክበዋል።
ለጉራጌ በቋንቋ፣ በባህልና በማኅበረሰብ ልማት ዘርፎች ያበረከቷቸው የሕይወት ዘመን አገልግሎቶች "አጋዝ" የሚል ባህላዊ ስያሜ የተሰጣቸው አጋዝ ገብረኢየሱስ ኃይለማርያም በጉራግኛ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ 16 መጽሐፍትን ጽፈዋል።
ለጉራጌ ባህልና ቋንቋ ልማት ካበረከቱት አስተዋጽኦ ባሻገር የጉራጌ ባህል ማእከል እና የጉራጌ ሕዝብ ራስ አገዝ ልማት ድርጅትን (ጉህራልድ) በምስረታ ሂደት ላይ ላቅ ያለ ሚና ነበራቸው። በሌሎች ሀገራዊና ዓለምአቀፍ ተቋማትም አሻራቸውን አኑረዋል።
በዚሁ ወቅት የብሔራዊ ቤተመዛግብት እና ቤተ መፅሀፍት አገልግሎት ፅህፈት ቤት ኅላፊ አቶ አባተ ካሣው እንደተናገሩት ደራሲገብረየሱስ በኢትዮጵያ በብሔረሰቦች ቋንቋ ድርሰት መጽሐፍ ከጀመሩት ውስጥ ናቸው ያሉ ሲሆን ታሪካዊ ሰነዶችን ለወመዘከወር በማስረከባቸው የተሰማንን ልባዊ ደስታ እንገልፃለን ብለዋል።
ለደራሲ ገብረየሱስም ከወመዘክር የተዘጋጀ የእውቅናና ምስጋና የምስክር ወረቀት ሰርተፊኬት ሰጥተዋል።
በዝግጅቱ ላይ የተገኙት የጉራጌ ዞን ባህልና ቱሪዝም መምሪያ ኃላፊ ወይዘሮ መሠረት አመርጋ በበኩላቸው እንዲህ አይነት ታሪካዊ ስራዎች በሰነድነት ታስበው የርክክብ ሥነ ሥርዓቱ መዘጋጀቱ ለሀገር ትልቅ ነገር ነው ብለዋል።
ደራሲ አጋዝ ገብረየሱስ ሀይለማርያም በበኩላቸው ስራዎቹን ሳከናውን እዚህ ይደርሳል ብዬ ባይሆንም የበርካታ ታሪክና ባለታሪኮች ሰነድ መገኛ የሆነው ወመዘክ ፎቶግራፎቼንና የድርሰት ስራዎቼን በአሻራነት መሰነድ በመቻሉ ደስታ ተሰምቶኛል ብለዋል።
ዝግጅቱ ተወዳጅ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን ከሶዶ ለማ ሚድያ ጋር በመተባበር አዘጋጅተውታል።
ዓለም አቀፍ የጉራጌ ማህበር - International Gurage Association - IGA
4 months ago
በአዲስ አበባ እና ሸገር ከተሞች የኃይል መቋረጥ ይኖራል፤ አካባቢዎን ያረጋግጡ!
ዛሬ ጥር 25 ቀን 2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በመሠረተ-ልማት የጥገና ሥራ ምክንያት በተለያዩ አካባቢዎች የኃይል አቅርቦት እንደሚቋረጥ አስታውቋል።
📍 የጊዜ ሰሌዳ
🔴 ከጠዋቱ 2:30 እስከ ቀኑ 11:00 ድረስ፦
ቦሌ አብሽሮ ሕንፃ፣ ገርጂ ጊዮርጊስ ሰፈር፣ ካሳንቺስ፣ ወረገኑ እና አካባቢው።
🔴 ከጠዋቱ 2:30 እስከ ቀኑ 9:30 ድረስ፦
ሴቶች አደባባይ፣ ካሳንቺስ መብራት ኃይል፣ ሂልተን ሆቴል ጀርባ፣ ኢንተር ኮንትኔንታል ሆቴል፣ ኢሊሌ ሆቴል፣ እናት ባንክ፣ ገነት ሆቴል፣ ጎፋ የጋራ መኖሪያ ቤቶች፣ ሐናን ዳቦ እና አካባቢው።
መካኒሳ፣ ቆሬ የጋራ መኖሪያ ቤቶች፣ ዶምቦስኮ ት/ቤት፣ ሚካኤል አደባባይ፣ ዩኒቲ ዩኒቨርስቲ፣ አንበሳ ጋራዥ፣ ጀርመን አደባባይ፣ ጉራጌ ሰፈር፣ ቆሼ፣ ሰሜን ማዘጋጃ እና ሸገር መናፈሻ።
ዕንቁላል ፋብሪካ፣ ሩፋኤል ቤተ-ክርስቲያን፣ ችሎት አደባባይ፣ ዘበኛ ሰፈር፣ ሾላ፣ ኢዜአ (ENA)፣ ሰሜን ሆቴል፣ ራስ ደስታ አካባቢ እና አርበኞች ት/ቤት።
🔴 ከረፋዱ 3:00 እስከ ቀኑ 9:00 ድረስ፦
ለገጣፎ፣ ሲዲሲ፣ ለገዳዲ፣ ሰንዳፋ ጫፍ፣ ኮካ ማዞሪያ፣ እንጦጦ ማርያም፣ ሽሮ ሜዳ፣ ስፔስ ሳይንስ፣ ሱሉልታ መሐል ከተማ፣ ጫንጮ አቢሲኒያ ሲሚንቶ እና አካባቢው።
🔴 ከጠዋቱ 2:00 እስከ ቀኑ 10:30 ድረስ፦
አቃቂ ኬላ፣ ገላን ኢንዱስትሪ መንደር ሙሉ፣ ወሰርቢ፣ ገላን ማዘጋጃ ቤት እና የገላን ኖክ ማደያ አካባቢ።
💡 ለተጠቃሚዎች ጠቃሚ ምክሮች
መብራት በሚቋረጥበት ወቅት የኤሌክትሪክ ቁሳቁሶችዎ ላይ ጉዳት እንዳይደርስ የሚከተሉትን ነጥቦች ልብ ይበሉ፦
መሣሪያዎችን ከሶኬት መንቀል፦ የኃይል አቅርቦቱ ሲመለስ ድንገተኛ ከፍተኛ የቮልቴጅ ጭማሪ (Power Surge) ሊኖር ስለሚችል፣ እንደ ፍሪጅ፣ ቴሌቪዥን እና ኮምፒውተር ያሉ መሣሪያዎችን አስቀድመው ይንቀሉ።
የኃይል ማከማቻዎችን ቻርጅ ማድረግ፦ ስልኮችን፣ ፓወር ባንኮችን እና የድንገተኛ ጊዜ መብራቶችን (Emergency Lights) አስቀድመው ቻርጅ በማድረግ ዝግጁ ይሁኑ።
የምግብ ደህንነት፦ የፍሪጅ መዝጊያዎችን ደጋግመው አይክፈቱ፤ ይህ ቅዝቃዜው ረዘም ላለ ጊዜ እንዲቆይና ምግቦች እንዳይበላሹ ይረዳል።
ማሳሰቢያ፦ የጥገና ሥራው እንደተጠናቀቀ የኃይል አቅርቦቱ ወዲያውኑ የሚመለስ ይሆናል።
📌 ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት
ዛሬ ጥር 25 ቀን 2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በመሠረተ-ልማት የጥገና ሥራ ምክንያት በተለያዩ አካባቢዎች የኃይል አቅርቦት እንደሚቋረጥ አስታውቋል።
📍 የጊዜ ሰሌዳ
🔴 ከጠዋቱ 2:30 እስከ ቀኑ 11:00 ድረስ፦
ቦሌ አብሽሮ ሕንፃ፣ ገርጂ ጊዮርጊስ ሰፈር፣ ካሳንቺስ፣ ወረገኑ እና አካባቢው።
🔴 ከጠዋቱ 2:30 እስከ ቀኑ 9:30 ድረስ፦
ሴቶች አደባባይ፣ ካሳንቺስ መብራት ኃይል፣ ሂልተን ሆቴል ጀርባ፣ ኢንተር ኮንትኔንታል ሆቴል፣ ኢሊሌ ሆቴል፣ እናት ባንክ፣ ገነት ሆቴል፣ ጎፋ የጋራ መኖሪያ ቤቶች፣ ሐናን ዳቦ እና አካባቢው።
መካኒሳ፣ ቆሬ የጋራ መኖሪያ ቤቶች፣ ዶምቦስኮ ት/ቤት፣ ሚካኤል አደባባይ፣ ዩኒቲ ዩኒቨርስቲ፣ አንበሳ ጋራዥ፣ ጀርመን አደባባይ፣ ጉራጌ ሰፈር፣ ቆሼ፣ ሰሜን ማዘጋጃ እና ሸገር መናፈሻ።
ዕንቁላል ፋብሪካ፣ ሩፋኤል ቤተ-ክርስቲያን፣ ችሎት አደባባይ፣ ዘበኛ ሰፈር፣ ሾላ፣ ኢዜአ (ENA)፣ ሰሜን ሆቴል፣ ራስ ደስታ አካባቢ እና አርበኞች ት/ቤት።
🔴 ከረፋዱ 3:00 እስከ ቀኑ 9:00 ድረስ፦
ለገጣፎ፣ ሲዲሲ፣ ለገዳዲ፣ ሰንዳፋ ጫፍ፣ ኮካ ማዞሪያ፣ እንጦጦ ማርያም፣ ሽሮ ሜዳ፣ ስፔስ ሳይንስ፣ ሱሉልታ መሐል ከተማ፣ ጫንጮ አቢሲኒያ ሲሚንቶ እና አካባቢው።
🔴 ከጠዋቱ 2:00 እስከ ቀኑ 10:30 ድረስ፦
አቃቂ ኬላ፣ ገላን ኢንዱስትሪ መንደር ሙሉ፣ ወሰርቢ፣ ገላን ማዘጋጃ ቤት እና የገላን ኖክ ማደያ አካባቢ።
💡 ለተጠቃሚዎች ጠቃሚ ምክሮች
መብራት በሚቋረጥበት ወቅት የኤሌክትሪክ ቁሳቁሶችዎ ላይ ጉዳት እንዳይደርስ የሚከተሉትን ነጥቦች ልብ ይበሉ፦
መሣሪያዎችን ከሶኬት መንቀል፦ የኃይል አቅርቦቱ ሲመለስ ድንገተኛ ከፍተኛ የቮልቴጅ ጭማሪ (Power Surge) ሊኖር ስለሚችል፣ እንደ ፍሪጅ፣ ቴሌቪዥን እና ኮምፒውተር ያሉ መሣሪያዎችን አስቀድመው ይንቀሉ።
የኃይል ማከማቻዎችን ቻርጅ ማድረግ፦ ስልኮችን፣ ፓወር ባንኮችን እና የድንገተኛ ጊዜ መብራቶችን (Emergency Lights) አስቀድመው ቻርጅ በማድረግ ዝግጁ ይሁኑ።
የምግብ ደህንነት፦ የፍሪጅ መዝጊያዎችን ደጋግመው አይክፈቱ፤ ይህ ቅዝቃዜው ረዘም ላለ ጊዜ እንዲቆይና ምግቦች እንዳይበላሹ ይረዳል።
ማሳሰቢያ፦ የጥገና ሥራው እንደተጠናቀቀ የኃይል አቅርቦቱ ወዲያውኑ የሚመለስ ይሆናል።
📌 ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት
4 months ago
የጥገና ሥራ ለማከናወን የሚቋረጥ የኃይል አቅርቦት
#ethiopia | ዛሬ ጥር 25 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ እና ሸገር ከተሞች የኃይል አቅርቦት የሚቋረጥባቸው አካባቢዎች፦
👉ከጠዋቱ 2:30 እስከ 11:00 ድረስ በቦሌ አብሽሮ ሕንፃ፣ በገርጂ ጊዮርጊስ ሰፈር፣ በካሳንቺስ ሰፈር፣ በወረገኑ እና አካባቢው፣
👉ከጠዋቱ 2:30 እስከ 9:30 ድረስ በሴቶች አደባባይ፣ በካሳንቺስ መብራት ኃይል፣ በሂልተን ሆቴል ጀርባ፣ በኢንተር ኮንትኔንታል ሆቴል፣ በሐናን ዳቦ፣ በኢሊሌ ሆቴል፣ በእናት ባንክ፣ በገነት ሆቴል፣ በአይናለም በዜ ሕንጻ ፣ በጎፋ የጋራ መኖሪያ ቤት፣ በጥቃቅንና አነስተኛ እና አካባቢው፣
👉በጎፋ ኪደነ ምህረት ቤተ-ክርስቲያን፣ በአሚጎ ካፌ፣ መካኒሳ፣ በቆሬ የጋራ መኖሪያ ቤቶች፣ በዶምቦስኮ ት/ቤት ፣ በሚካኤል አደባባይ በቆሬ የጋራ መኖረያ ቤቶች ፣ በዩኒቲ ዩኒቨርስቲ፣ በአንበሳ ጋራዥ፣ በጀርመን አደባባይ፣ በጉራጌ ሰፈር፣ በትግሬ ሰፈር፣ በካፍ ነዳጅ ማደያ ጀርባ፣ በአርሴማ ቤተ-ክርስቲያን፣ በምስራቀ ገብርኤል፣ በጀርመን አደባባይ፣ በቆሼ፣ በሰሜን ማዘጋጃ፣ በሸገር መናፈሻ እና አካባቢው፣
👉 በመስቀሉ ሥጋ ቤት፣ በዳዊት ፋርማሲ፣ በዕንቁላል ፋብሪካ፣ በአባዲና፣ በሩፋኤል ቤተ-ክርስቲያን፣ በችሎት አደባባይ፣ በዘበኛ ሰፈር፣ በሾላ፣ በኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት፣ በሰሜን ሆቴል ጫፍ፣ በቀለመ-ወርቅ ት/ቤት፣ በዶሮ ተራ፣ በራስ ደስታ አካባቢ፣ በአርበኞች ት/ቤት እና አካባቢው፣
👉ከረፋዱ 3:00 እስከ ቀኑ 9:00 በለገጣፎ፣ በሲዲሲ፣ በኮሰሮ፣ በለገዳዲ፣ በ44 ማዞሪያ፣ በኤሞሌስ ፋብሪካ፣ በካሰዴ፣ በጣፎ፣ በሰንዳፋ ጫፍ፣ በኮካ ማዞሪያ፣ በፍተሻ አካባቢ፣ በእንጦጦ ማርያም ቤተ-ክርስቲያን፣ በሽሮ ሜዳ፣ በስፔስ ሳይንስ፣ በሽንቁሩ ሚካኤል፣ በአካኮ ገብርኤል፣ በ10 ኪሎ ፣ በዶሮ እርባታ፣ በቀንብሬ፣ በአፍሪካ ልሕቀት ማዕከል፣ በአርኪ ውሃ፣ በሱሉልታ መሐል ከተማ፣ በለገዲማ፣ በጫንጮ አቢሲኒያ ሲሚንቶ እና አካባቢው፣
👉ከጠዋቱ 2:00 እስከ 10:30 በአቃቂ ኬላ፣ በገላን ኢንዱስትሪ መንደር ሙሉ፣ በወሰርቢ፣ በገላን ማዘጋጃ ቤት ፣ በፒኤልሲ፣ በነጮ፣ በኖክ ማደያ እና አካባቢው የጥገና ሥራ ስለሚከናዎን የኃይል አቅርቦቱ የሚቋረጥ ይሆናል፡፡
ስለሆነም በተጠቀሱት አካባቢዎች የምትገኙ ክቡራን ደንበኞቻችን የጥገና ሥራው ተጠናቆ የኃይል አቅርቦቱ እስኪ መለስ ድረስ በትዕግስት እንድትጠብቁን በትህትና እንጠይቃለን።
(የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት)
#ethiopia | ዛሬ ጥር 25 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ እና ሸገር ከተሞች የኃይል አቅርቦት የሚቋረጥባቸው አካባቢዎች፦
👉ከጠዋቱ 2:30 እስከ 11:00 ድረስ በቦሌ አብሽሮ ሕንፃ፣ በገርጂ ጊዮርጊስ ሰፈር፣ በካሳንቺስ ሰፈር፣ በወረገኑ እና አካባቢው፣
👉ከጠዋቱ 2:30 እስከ 9:30 ድረስ በሴቶች አደባባይ፣ በካሳንቺስ መብራት ኃይል፣ በሂልተን ሆቴል ጀርባ፣ በኢንተር ኮንትኔንታል ሆቴል፣ በሐናን ዳቦ፣ በኢሊሌ ሆቴል፣ በእናት ባንክ፣ በገነት ሆቴል፣ በአይናለም በዜ ሕንጻ ፣ በጎፋ የጋራ መኖሪያ ቤት፣ በጥቃቅንና አነስተኛ እና አካባቢው፣
👉በጎፋ ኪደነ ምህረት ቤተ-ክርስቲያን፣ በአሚጎ ካፌ፣ መካኒሳ፣ በቆሬ የጋራ መኖሪያ ቤቶች፣ በዶምቦስኮ ት/ቤት ፣ በሚካኤል አደባባይ በቆሬ የጋራ መኖረያ ቤቶች ፣ በዩኒቲ ዩኒቨርስቲ፣ በአንበሳ ጋራዥ፣ በጀርመን አደባባይ፣ በጉራጌ ሰፈር፣ በትግሬ ሰፈር፣ በካፍ ነዳጅ ማደያ ጀርባ፣ በአርሴማ ቤተ-ክርስቲያን፣ በምስራቀ ገብርኤል፣ በጀርመን አደባባይ፣ በቆሼ፣ በሰሜን ማዘጋጃ፣ በሸገር መናፈሻ እና አካባቢው፣
👉 በመስቀሉ ሥጋ ቤት፣ በዳዊት ፋርማሲ፣ በዕንቁላል ፋብሪካ፣ በአባዲና፣ በሩፋኤል ቤተ-ክርስቲያን፣ በችሎት አደባባይ፣ በዘበኛ ሰፈር፣ በሾላ፣ በኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት፣ በሰሜን ሆቴል ጫፍ፣ በቀለመ-ወርቅ ት/ቤት፣ በዶሮ ተራ፣ በራስ ደስታ አካባቢ፣ በአርበኞች ት/ቤት እና አካባቢው፣
👉ከረፋዱ 3:00 እስከ ቀኑ 9:00 በለገጣፎ፣ በሲዲሲ፣ በኮሰሮ፣ በለገዳዲ፣ በ44 ማዞሪያ፣ በኤሞሌስ ፋብሪካ፣ በካሰዴ፣ በጣፎ፣ በሰንዳፋ ጫፍ፣ በኮካ ማዞሪያ፣ በፍተሻ አካባቢ፣ በእንጦጦ ማርያም ቤተ-ክርስቲያን፣ በሽሮ ሜዳ፣ በስፔስ ሳይንስ፣ በሽንቁሩ ሚካኤል፣ በአካኮ ገብርኤል፣ በ10 ኪሎ ፣ በዶሮ እርባታ፣ በቀንብሬ፣ በአፍሪካ ልሕቀት ማዕከል፣ በአርኪ ውሃ፣ በሱሉልታ መሐል ከተማ፣ በለገዲማ፣ በጫንጮ አቢሲኒያ ሲሚንቶ እና አካባቢው፣
👉ከጠዋቱ 2:00 እስከ 10:30 በአቃቂ ኬላ፣ በገላን ኢንዱስትሪ መንደር ሙሉ፣ በወሰርቢ፣ በገላን ማዘጋጃ ቤት ፣ በፒኤልሲ፣ በነጮ፣ በኖክ ማደያ እና አካባቢው የጥገና ሥራ ስለሚከናዎን የኃይል አቅርቦቱ የሚቋረጥ ይሆናል፡፡
ስለሆነም በተጠቀሱት አካባቢዎች የምትገኙ ክቡራን ደንበኞቻችን የጥገና ሥራው ተጠናቆ የኃይል አቅርቦቱ እስኪ መለስ ድረስ በትዕግስት እንድትጠብቁን በትህትና እንጠይቃለን።
(የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት)
4 months ago
📚 የ"አጋዝ" ስራዎች ለትውልድ ሊቀመጡ ነው!
"ድንቁን ቅፅበት ለማወቅ ይታደሙ!"
#ethiopia | በቋንቋ፣ በባህልና በማኅበረሰብ ልማት ዘርፎች ባበረከቱት የጎላ አስተዋጽኦ "አጋዝ" የሚል የክብር ስያሜ የተሰጣቸው የደራሲ አጋዝ ገብረየሱስ ኃይለማሪያም ስራዎች ለብሄራዊ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት ኤጀንሲ (ወመዘክር) ሊበረከቱ ነው።
ስለ አጋዝ ገብረየሱስ:
✅ በጉራግኛ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋዎች 16 መጽሐፍትን ጽፈዋል።
✅ የጉራጌ ሕዝብ ራስ አገዝ ልማት ድርጅትን (ገህራልድ) መስራች እና አገልጋይ ነበሩ።
✅ ለጉራጌ ባህልና ቋንቋ እንዲሁም ለሀገር ልማት አሻራቸውን አኑረዋል።
የመርሐ ግብሩ ዝርዝር:
ተወዳጅ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን ከሶዶ ለማ ሚድያ ጋር በመተባበር ባዘጋጁት በዚህ ታላቅ መድረክ ላይ፤ የደራሲው ስራዎች ለትውልድ ማስታወሻነት ለወመዘክር በክብር ይሰጣሉ።
📅 ቀን: ቅዳሜ ጥር 23 ቀን 2018 ዓ.ም
clock ሰዓት: ከረፋዱ 4:00 ጀምሮ
📍 ቦታ: ወመዘክር (ብሔራዊ ቤተ-መጻሕፍት)፣ ኅሩይ አዳራሽ
የታሪክ እና የስነ-ጽሑፍ ወዳጆች በዚህ ታሪካዊ ቅጽበት እንድትገኙ ተጋብዛችኋል!
#agazgebreyesus #literature #history #wemezekir #gurageculture #bookdonation #ethiopia #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን
"ድንቁን ቅፅበት ለማወቅ ይታደሙ!"
#ethiopia | በቋንቋ፣ በባህልና በማኅበረሰብ ልማት ዘርፎች ባበረከቱት የጎላ አስተዋጽኦ "አጋዝ" የሚል የክብር ስያሜ የተሰጣቸው የደራሲ አጋዝ ገብረየሱስ ኃይለማሪያም ስራዎች ለብሄራዊ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት ኤጀንሲ (ወመዘክር) ሊበረከቱ ነው።
ስለ አጋዝ ገብረየሱስ:
✅ በጉራግኛ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋዎች 16 መጽሐፍትን ጽፈዋል።
✅ የጉራጌ ሕዝብ ራስ አገዝ ልማት ድርጅትን (ገህራልድ) መስራች እና አገልጋይ ነበሩ።
✅ ለጉራጌ ባህልና ቋንቋ እንዲሁም ለሀገር ልማት አሻራቸውን አኑረዋል።
የመርሐ ግብሩ ዝርዝር:
ተወዳጅ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን ከሶዶ ለማ ሚድያ ጋር በመተባበር ባዘጋጁት በዚህ ታላቅ መድረክ ላይ፤ የደራሲው ስራዎች ለትውልድ ማስታወሻነት ለወመዘክር በክብር ይሰጣሉ።
📅 ቀን: ቅዳሜ ጥር 23 ቀን 2018 ዓ.ም
clock ሰዓት: ከረፋዱ 4:00 ጀምሮ
📍 ቦታ: ወመዘክር (ብሔራዊ ቤተ-መጻሕፍት)፣ ኅሩይ አዳራሽ
የታሪክ እና የስነ-ጽሑፍ ወዳጆች በዚህ ታሪካዊ ቅጽበት እንድትገኙ ተጋብዛችኋል!
#agazgebreyesus #literature #history #wemezekir #gurageculture #bookdonation #ethiopia #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን
Sponsored by
Surafel
4 months ago
4 months ago
በጉራጌ ሀገረ ስብክት የምትገኘው ቆጠር ገድራ ቅድስት ኪዳነ ምህረት ቤተክርስቲያን የገቢ ማሰባሰቢያ መርሀ-ግብር ተዘጋጀ!
በጉራጌ ሀገረ ስብክት የምትገኘው ቆጠር ገድራ ቅድስት ኪዳነ ምህረት ቤተክርስትያን በበጎ አባቶች እና በምዕመናን እነሳሽነት እየታነፀች ትገኛለች የተጀመረውን ሕንፃ ቤተክርስቲያን ለማስፈጸም ከጥር 29 እስከ የካቲት 01/2018 ለሦስት ተከታታይ ቀናት የሚቆይ የቀጥታ ሥርጭት የገቢ ማሰባሰቢያ መርሐግብር መዘጋጀቱ ተገልጿል፡፡
የቀጥታ ስርጭት መርሀ-ግብሩ በወልቂጤ ከተማ እንደሚካሄድም ተገልጿል።
ይህ ቤተ ክርስቲያን በዕድሜ ብዛት በመጎዳቱ በየጊዜው ዕድሳት እየተደረገለት እስከዛሬ መቆየቱ ተገልፆ በአሁኑ ሰዓትም ለበርካታ ሕዝበ ክርስቲያን አገልግሎት በመስጠት ላይ እንደሚገኝ ተገልጿል።
ቆጠር, የሚለው ቃል ቦታውን የመሠረቱት ግለሰብ ስም ሲኾን፣ በጊዜ ሒደት ቃሉ የጎሣ መጠርያ ኾኖ ቀጥሏል። ገድራ, በአካባቢው ቋንቋ የዛፍ ዓይነትን የሚያመለክት ቃል ነው።
በቆጠር ገድራ በአንድ ወቅት በተደረገ ቁፋሮ ሰባት ጥንታውያን የዋሻ ቤተ መቅደሶች፣ ሦስት የሱባዔ መያዣ ቦታዎችና ልዩ ልዩ ንዋያተ ቅድሳት ተገኝተዋል፡፡
ይህም በዚያ ሥፍራ ቀደም ሲል ቤተ ክርስቲያን ታንጾ እንደ ነበር የሚጠቁም ማስረጃ መሆኑ እና በቁፋሮ የተገኙ ሰባቱ የዋሻ ቤተ መቅደሶችም:- የደብረ ቢዘን ቤተ መቅደስ፣ ቤተ ጎልጎታ፣ ቤተ መድኅን፣ ቤተ ጠበብት፣ ቤተ ኤፍራታ፣ ቤተ ደብረ ብርሃን እና ቤተ ደናግል ይባላሉ።
ከእነዚህ ቤተ መቅደሶች መካከል በቤተ ጎልጎታ የኦሪት መሥዋዕት ይቀርብበት እንደ ነበረ፤ በውስጡም ከወርቅ የተሠራ መሠዊያ እንደ ተገኘና ይህን መሠዊያም በስድስተኛው መቶ ክፍለ ዘመን በሥፍራው ሲያገለግሉ የነበሩ አባ ማትያስ የተባሉ አባት እንዳይዘረፍ ብለው ቆፈረው እንደ ቀበሩት የአካባቢውን ታሪክ የሚያውቁ አባቶች ይናገራሉ፡፡
በመሆኑም በበኩረ ምእመናን ቀኝ አዝማች ትዕዛዙ ኮሬ ሰብሳቢነት፣ በአካባቢው ተወላጆች፣ በደጋግ የጉራጌ ማኅበረሰብ እና በመላው ዓለም በሚገኙ ኦርቶዶክሳውያን የኪዳነ ምሕረት ወዳጆች የተጀመረው ይህ ገዳሙን የማሳደግ ሥራ ዓላማው በየጊዜው እየቀዘቀዘ የመጣውን የአብነት ትምህርት ለማስፋፋት፣ ጥንታውያን ቅርሶችን በመጠበቅ ለትውልድ ለማስተላለፍ፣ የቅድስት ቤተ ክርስቲያንን አገልግሎት ለማሳደግ፣ ስብከተ ወንጌልን በስፋት ለማዳረስ በተጠቀሰዉ ቀን እና ሰአት በተዘጋጀዉ ቀጥታ ስርጭት ሁላችሁም በመገኘት የበኩላችሁን እንድትወጡ ጥሪ ቀርቧል።
ስልክ
0911512707
0913380901
0911751529
ባንክ አካውንት፦1000257570103 ቆጠር ገድራ መካነ ቅዱሳን ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ገዳም
በጉራጌ ሀገረ ስብክት የምትገኘው ቆጠር ገድራ ቅድስት ኪዳነ ምህረት ቤተክርስትያን በበጎ አባቶች እና በምዕመናን እነሳሽነት እየታነፀች ትገኛለች የተጀመረውን ሕንፃ ቤተክርስቲያን ለማስፈጸም ከጥር 29 እስከ የካቲት 01/2018 ለሦስት ተከታታይ ቀናት የሚቆይ የቀጥታ ሥርጭት የገቢ ማሰባሰቢያ መርሐግብር መዘጋጀቱ ተገልጿል፡፡
የቀጥታ ስርጭት መርሀ-ግብሩ በወልቂጤ ከተማ እንደሚካሄድም ተገልጿል።
ይህ ቤተ ክርስቲያን በዕድሜ ብዛት በመጎዳቱ በየጊዜው ዕድሳት እየተደረገለት እስከዛሬ መቆየቱ ተገልፆ በአሁኑ ሰዓትም ለበርካታ ሕዝበ ክርስቲያን አገልግሎት በመስጠት ላይ እንደሚገኝ ተገልጿል።
ቆጠር, የሚለው ቃል ቦታውን የመሠረቱት ግለሰብ ስም ሲኾን፣ በጊዜ ሒደት ቃሉ የጎሣ መጠርያ ኾኖ ቀጥሏል። ገድራ, በአካባቢው ቋንቋ የዛፍ ዓይነትን የሚያመለክት ቃል ነው።
በቆጠር ገድራ በአንድ ወቅት በተደረገ ቁፋሮ ሰባት ጥንታውያን የዋሻ ቤተ መቅደሶች፣ ሦስት የሱባዔ መያዣ ቦታዎችና ልዩ ልዩ ንዋያተ ቅድሳት ተገኝተዋል፡፡
ይህም በዚያ ሥፍራ ቀደም ሲል ቤተ ክርስቲያን ታንጾ እንደ ነበር የሚጠቁም ማስረጃ መሆኑ እና በቁፋሮ የተገኙ ሰባቱ የዋሻ ቤተ መቅደሶችም:- የደብረ ቢዘን ቤተ መቅደስ፣ ቤተ ጎልጎታ፣ ቤተ መድኅን፣ ቤተ ጠበብት፣ ቤተ ኤፍራታ፣ ቤተ ደብረ ብርሃን እና ቤተ ደናግል ይባላሉ።
ከእነዚህ ቤተ መቅደሶች መካከል በቤተ ጎልጎታ የኦሪት መሥዋዕት ይቀርብበት እንደ ነበረ፤ በውስጡም ከወርቅ የተሠራ መሠዊያ እንደ ተገኘና ይህን መሠዊያም በስድስተኛው መቶ ክፍለ ዘመን በሥፍራው ሲያገለግሉ የነበሩ አባ ማትያስ የተባሉ አባት እንዳይዘረፍ ብለው ቆፈረው እንደ ቀበሩት የአካባቢውን ታሪክ የሚያውቁ አባቶች ይናገራሉ፡፡
በመሆኑም በበኩረ ምእመናን ቀኝ አዝማች ትዕዛዙ ኮሬ ሰብሳቢነት፣ በአካባቢው ተወላጆች፣ በደጋግ የጉራጌ ማኅበረሰብ እና በመላው ዓለም በሚገኙ ኦርቶዶክሳውያን የኪዳነ ምሕረት ወዳጆች የተጀመረው ይህ ገዳሙን የማሳደግ ሥራ ዓላማው በየጊዜው እየቀዘቀዘ የመጣውን የአብነት ትምህርት ለማስፋፋት፣ ጥንታውያን ቅርሶችን በመጠበቅ ለትውልድ ለማስተላለፍ፣ የቅድስት ቤተ ክርስቲያንን አገልግሎት ለማሳደግ፣ ስብከተ ወንጌልን በስፋት ለማዳረስ በተጠቀሰዉ ቀን እና ሰአት በተዘጋጀዉ ቀጥታ ስርጭት ሁላችሁም በመገኘት የበኩላችሁን እንድትወጡ ጥሪ ቀርቧል።
ስልክ
0911512707
0913380901
0911751529
ባንክ አካውንት፦1000257570103 ቆጠር ገድራ መካነ ቅዱሳን ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ገዳም
5 months ago
🍽️ ክትፎን ጨምሮ አራት የጉራጌ ዕሴቶች ወደ ዩኔስኮ (UNESCO) ሊያመሩ ነው
#ethiopia | የጉራጌ ዞን ባህልና ቱሪዝም መምሪያ፣ ታዋቂውን የጉራጌ ክትፎን ጨምሮ አራት የጉራጌ ባህላዊ እሴቶችን በዓለም የማይዳሰሱ ቅርሶች ዝርዝር ውስጥ ለማስመዝገብ ጥናት መጀመሩን አስታወቀ።
🥩 ክትፎ፦ ከምግብነት በላይ የሆነ የማንነት መገለጫ
የጉራጌ ክትፎ በዩኔስኮ ቅድሚያ ከተሰጣቸው እሴቶች መካከል ቀዳሚው ነው። ክትፎ ለጉራጌ ማህበረሰብ ምግብ ብቻ ሳይሆን የእንግዳ መቀበያ፣ የማህበራዊ ትስስር እና የጥበብ መገለጫ ነው። በአሁኑ ወቅት የክትፎ አዘገጃጀት፣ ከቆጮ፣ ከሚጥሚጣ እና ከንጥር ቅቤ ጋር ያለው ቁርኝት በጥልቀት እየተጠና ይገኛል።
📜 ሊመዘገቡ የታጩት አራት የኩራት ምንጮች፦
* የክትፎ አዘገጃጀት ጥበብ፦ ልዩ የሆነው የማክተፍ፣ የቅመማ ቅመም አጠቃቀምና የማቅረብ ስነስርዓት።
* ባህላዊ የክብ ቤት አሰራር፦ ያለ ሚስማር የሚገነባውና ለዘመናት የሚቆየው፣ የምህንድስና ጥበብ የታየበት የቤት አሰራር።
* የጎርደና የዳኝነት ስርአት፦ ለማህበራዊ ሰላምና ፍትህ የሚጠቀሙበት ጥንታዊና ውጤታማ የዳኝነት ስርዓት።
* የጀፎረ (መንደር) አወቃቀር፦ ለጋራ መስተጋብር በሚመች መልኩ የሚሰሩ ሰፋፊ መንገዶችና ማራኪ የመንደር አቀማመጥ።
📍 የጥናቱ ሂደት ምን ደረጃ ላይ ይገኛል?
የመምሪያው ኃላፊ ወይዘሮ መሰረት አመረጋ እንደገለጹት፣ ለኢትዮጵያ ቅርስ ጥበቃ ባለስልጣን የቀረበው ጥያቄ ተቀባይነት አግኝቷል። ጥናቱ እንደተጠናቀቀ ሰነዱ በቀጥታ በፈረንሳይ ፓሪስ ለሚገኘው የዩኔስኮ ዋና መስሪያ ቤት ለውሳኔ ይላካል።
ከዚህ በተጨማሪ በዞኑ የሚገኙ ዕድሜ ጠገብ መስጂዶች፣ ጥንታዊ ኪታቦች፣ ገዳማትና ታሪካዊ ዋሻዎች ለቱሪስት መስህብነት እንዲውሉ በትኩረት እየተሰራ መሆኑ ተገልጿል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#ጉራጌ #ክትፎ #ዩኔስኮ #ቅርስ #ኢትዮጵያ #ባህል #ቱሪዝም #የጉራጌባህል #gurage #kitfo #unesco #ethiopianheritage #tourismethiopia
#ethiopia | የጉራጌ ዞን ባህልና ቱሪዝም መምሪያ፣ ታዋቂውን የጉራጌ ክትፎን ጨምሮ አራት የጉራጌ ባህላዊ እሴቶችን በዓለም የማይዳሰሱ ቅርሶች ዝርዝር ውስጥ ለማስመዝገብ ጥናት መጀመሩን አስታወቀ።
🥩 ክትፎ፦ ከምግብነት በላይ የሆነ የማንነት መገለጫ
የጉራጌ ክትፎ በዩኔስኮ ቅድሚያ ከተሰጣቸው እሴቶች መካከል ቀዳሚው ነው። ክትፎ ለጉራጌ ማህበረሰብ ምግብ ብቻ ሳይሆን የእንግዳ መቀበያ፣ የማህበራዊ ትስስር እና የጥበብ መገለጫ ነው። በአሁኑ ወቅት የክትፎ አዘገጃጀት፣ ከቆጮ፣ ከሚጥሚጣ እና ከንጥር ቅቤ ጋር ያለው ቁርኝት በጥልቀት እየተጠና ይገኛል።
📜 ሊመዘገቡ የታጩት አራት የኩራት ምንጮች፦
* የክትፎ አዘገጃጀት ጥበብ፦ ልዩ የሆነው የማክተፍ፣ የቅመማ ቅመም አጠቃቀምና የማቅረብ ስነስርዓት።
* ባህላዊ የክብ ቤት አሰራር፦ ያለ ሚስማር የሚገነባውና ለዘመናት የሚቆየው፣ የምህንድስና ጥበብ የታየበት የቤት አሰራር።
* የጎርደና የዳኝነት ስርአት፦ ለማህበራዊ ሰላምና ፍትህ የሚጠቀሙበት ጥንታዊና ውጤታማ የዳኝነት ስርዓት።
* የጀፎረ (መንደር) አወቃቀር፦ ለጋራ መስተጋብር በሚመች መልኩ የሚሰሩ ሰፋፊ መንገዶችና ማራኪ የመንደር አቀማመጥ።
📍 የጥናቱ ሂደት ምን ደረጃ ላይ ይገኛል?
የመምሪያው ኃላፊ ወይዘሮ መሰረት አመረጋ እንደገለጹት፣ ለኢትዮጵያ ቅርስ ጥበቃ ባለስልጣን የቀረበው ጥያቄ ተቀባይነት አግኝቷል። ጥናቱ እንደተጠናቀቀ ሰነዱ በቀጥታ በፈረንሳይ ፓሪስ ለሚገኘው የዩኔስኮ ዋና መስሪያ ቤት ለውሳኔ ይላካል።
ከዚህ በተጨማሪ በዞኑ የሚገኙ ዕድሜ ጠገብ መስጂዶች፣ ጥንታዊ ኪታቦች፣ ገዳማትና ታሪካዊ ዋሻዎች ለቱሪስት መስህብነት እንዲውሉ በትኩረት እየተሰራ መሆኑ ተገልጿል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#ጉራጌ #ክትፎ #ዩኔስኮ #ቅርስ #ኢትዮጵያ #ባህል #ቱሪዝም #የጉራጌባህል #gurage #kitfo #unesco #ethiopianheritage #tourismethiopia
5 months ago
የጉራጌ ክትፎ ወደ ዩኔስኮ የዓለም ቅርስነት! 🇪🇹🍲✨
ታዋቂው የጉራጌ ክትፎን ጨምሮ አራት የጉራጌ ባህላዊ እሴቶችን በተባበሩት መንግስታት የትምህርት፣ ሳይንስና ባህል ድርጅት (UNESCO) በዓለም የማይዳሰሱ ቅርሶች ዝርዝር ውስጥ ለማስመዝገብ ጥናት መጀመሩን የዞኑ ባህልና ቱሪዝም መምሪያ አስታወቀ።
🔹 ለምን ክትፎ ቅድሚያ ተሰጠው?
ክትፎ ከምግብነቱ ባለፈ የጉራጌ ማህበረሰብ መገለጫ፣ የእንግዳ መቀበያ እና የማህበራዊ ትስስር እሴት በመሆኑ ነው። በአሁኑ ወቅት የክትፎ አዘገጃጀት፣ የሚያስፈልጉ ግብዓቶች (እንደ ቆጮ፣ ሚጥሚጣ እና ንጥር ቅቤ) ያላቸውን ጥበብ በማካተት ሰፊ ጥናት እየተደረገ ይገኛል።
🔹 ሊመዘገቡ የታጩ አራት እሴቶች፦
1️⃣ የጉራጌ ክትፎ አዘገጃጀት፦ ልዩ የሆነው የማክተፍ እና የቅመማ ቅመም ጥበብ።
2️⃣ ባህላዊ የቤት አሰራር (ክብ ቤት)፦ ያለ ሚስማር የሚገነባውና ለዘመናት የሚቆየው የቤት አሰራር ጥበብ።
3️⃣ ባህላዊ የዳኝነት ስርዓት (የጎርደና ስርአት)፦ ማህበራዊ ሰላምን ለማስፈን የሚጠቀሙበት ጥንታዊ የፍትህ ስርአት።
4️⃣ የጉራጌ መንደር (ጀፎረ) አሰራር፦ ለጋራ መስተጋብር በሚመች መልኩ የሚሰሩ ሰፋፊ መንገዶችና የመንደር አወቃቀር።
📍 የጥናቱ ሂደት
የጉራጌ ዞን ባህልና ቱሪዝም መምሪያ ኃላፊ ወይዘሮ መሰረት አመረጋ እንደገለጹት፣ ለኢትዮጵያ ቅርስ ጥበቃ ባለስልጣን የቀረበው ጥያቄ ተቀባይነት አግኝቷል። ጥናቱ እንደተጠናቀቀም ሰነዱ ለዩኔስኮ ዋና መስሪያ ቤት ለውሳኔ ይላካል።
🔹 ሌሎች የሚጠበቁ ቅርሶች
በዞኑ የሚገኙ ታሪካዊ ዋሻዎች፣ በዕድሜ ጠገብ መስጂዶች የሚገኙ ጥንታዊ ኪታቦች እና በገዳማት የሚገኙ ንዋየ ቅድሳት ለቱሪስት መስህብነት እንዲውሉና ጥበቃ እንዲደረግላቸው በትኩረት እየተሰራ መሆኑ ተገልጿል።
ብስራት ራዲዮ
ታዋቂው የጉራጌ ክትፎን ጨምሮ አራት የጉራጌ ባህላዊ እሴቶችን በተባበሩት መንግስታት የትምህርት፣ ሳይንስና ባህል ድርጅት (UNESCO) በዓለም የማይዳሰሱ ቅርሶች ዝርዝር ውስጥ ለማስመዝገብ ጥናት መጀመሩን የዞኑ ባህልና ቱሪዝም መምሪያ አስታወቀ።
🔹 ለምን ክትፎ ቅድሚያ ተሰጠው?
ክትፎ ከምግብነቱ ባለፈ የጉራጌ ማህበረሰብ መገለጫ፣ የእንግዳ መቀበያ እና የማህበራዊ ትስስር እሴት በመሆኑ ነው። በአሁኑ ወቅት የክትፎ አዘገጃጀት፣ የሚያስፈልጉ ግብዓቶች (እንደ ቆጮ፣ ሚጥሚጣ እና ንጥር ቅቤ) ያላቸውን ጥበብ በማካተት ሰፊ ጥናት እየተደረገ ይገኛል።
🔹 ሊመዘገቡ የታጩ አራት እሴቶች፦
1️⃣ የጉራጌ ክትፎ አዘገጃጀት፦ ልዩ የሆነው የማክተፍ እና የቅመማ ቅመም ጥበብ።
2️⃣ ባህላዊ የቤት አሰራር (ክብ ቤት)፦ ያለ ሚስማር የሚገነባውና ለዘመናት የሚቆየው የቤት አሰራር ጥበብ።
3️⃣ ባህላዊ የዳኝነት ስርዓት (የጎርደና ስርአት)፦ ማህበራዊ ሰላምን ለማስፈን የሚጠቀሙበት ጥንታዊ የፍትህ ስርአት።
4️⃣ የጉራጌ መንደር (ጀፎረ) አሰራር፦ ለጋራ መስተጋብር በሚመች መልኩ የሚሰሩ ሰፋፊ መንገዶችና የመንደር አወቃቀር።
📍 የጥናቱ ሂደት
የጉራጌ ዞን ባህልና ቱሪዝም መምሪያ ኃላፊ ወይዘሮ መሰረት አመረጋ እንደገለጹት፣ ለኢትዮጵያ ቅርስ ጥበቃ ባለስልጣን የቀረበው ጥያቄ ተቀባይነት አግኝቷል። ጥናቱ እንደተጠናቀቀም ሰነዱ ለዩኔስኮ ዋና መስሪያ ቤት ለውሳኔ ይላካል።
🔹 ሌሎች የሚጠበቁ ቅርሶች
በዞኑ የሚገኙ ታሪካዊ ዋሻዎች፣ በዕድሜ ጠገብ መስጂዶች የሚገኙ ጥንታዊ ኪታቦች እና በገዳማት የሚገኙ ንዋየ ቅድሳት ለቱሪስት መስህብነት እንዲውሉና ጥበቃ እንዲደረግላቸው በትኩረት እየተሰራ መሆኑ ተገልጿል።
ብስራት ራዲዮ
Sponsored by
Surafel
Comments