1 day ago
የኢራን ፓርላማ አሜሪካ እና እስራኤል በሆርሙዝ ወሽመጥ እንዳያልፉ የሚከለክል ረቂቅ ሕግ አቀረበ
የኢራን ፓርላማ በሆርሙዝ ወሽመጥ በኩል እና በፐርዢያ ባሕረ ሰላጤ በኩል የሚያልፉ መርከቦች ላይ ያለውን ቁጥጥር የሚያጠብቅ ረቂቅ ሕግ ላይ ተወያየ።
ረቂቅ ሕጉ ከአሜሪካ፣ እስራኤል እና ቴህራን ጠብ አጫሪ ናቸው ስትል ከምትፈርጃቸው አገራት ጋር ግንኙነት ያላቸው መርከቦችን ማገድ እንደሚያካትት ታስኒም የዜና ወኪል ዘግቧል።
ታስኒም የፓርላማ አባል የሆኑትን አባስ ሳሊሚን ጠቅሶ እንደዘገበው የፓርላማው ብሔራዊ ደህንነት እና የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ኮሚቴ በወሽመጡ እና በፐርዢያ ባሕረ ሰላጤ ላይ አገሪቱ የሚኖራትን ቁጥጥር በሚመለከት ተወያይቷል።
በረቂቅ ሕጉ መሠረት አሜሪካ፣ እስራኤል እና ኢራን ጠብ አጫሪ ብላ ከፈረጀቻቸው ሌሎች አገራት ጋር ግንኙነት ያላቸውን መርከቦች በወሽመጡ እንዳያልፉ ይከለከላከሉ።
በረቂቅ ሕጉ በተጨማሪም ከእስራኤል ገር ግንኙነት ያላቸው ወታደራዊ እና የሲቪል የጭነት መርከቦች እንዲሁም በኢራን ላይ በተከፈተው ዘመቻ ድጋፍ ያደረጉ እንዳያልፉ ይከለከላሉ።
በተጨማሪም በኢራን ላይ ጉዳት በማድረስ ረገድ ኃላፊነት አለባቸው ተብለው የሚታመኑ አገራትና ግለሰቦች፣ ካሳ እስኪከፍሉ ድረስ በሆርሙዝ የባሕር ወሽመጥ እና በፋርስ ባሕረ ሰላጤ በኩል የማለፍ ፈቃድ አይሰጣቸውም።
ረቂቅ ሕጉ ለሚፈጸሙ ጥሰቶች ከባድ ቅጣቶችን፤ ከእነዚህም መካከል በመርከብ ላይ የተጫነው ሸቀጥ ካለው ዋጋ እስከ 20 በመቶ የሚደርስ የገንዘብ ቅጣትን አካትቷል።
በሕጉ መሠረት፣ መንግሥት በፋርስ ባህረ ሰላጤ ውስጥ የአሰሳ ስራን ለመቆጣጠር፣ የመርከቦችን እንቅስቃሴ ለመከታተል እንዲሁም ደህንነትን እና የአካባቢ ጥበቃን ለማረጋገጥ ከጦር ኃይሎች ጋር በጋራ እንዲሰራ ይጠበቅበታል።
ሳሊም ሕጉ በባለሙያዎች እየታየ መሆኑን እና ከመጽደቁ በፊት የማሻሻያ ሃሳባቸውን እንዲያቀርቡ ይጠበቃል ብለዋል።
የኢራን ፓርላማ ረቂቅ ሕጉ ላይ የተወያየው አገሪቱ ከኦማን ጋር በወሽመጡ አስተዳደር ላይ እየተነጋገረች ባለችበት እና ከሥምምነት ይደረሳል ተብሎ በሚጠበቅበት ወቅት ነው።
BBC
የኢራን ፓርላማ በሆርሙዝ ወሽመጥ በኩል እና በፐርዢያ ባሕረ ሰላጤ በኩል የሚያልፉ መርከቦች ላይ ያለውን ቁጥጥር የሚያጠብቅ ረቂቅ ሕግ ላይ ተወያየ።
ረቂቅ ሕጉ ከአሜሪካ፣ እስራኤል እና ቴህራን ጠብ አጫሪ ናቸው ስትል ከምትፈርጃቸው አገራት ጋር ግንኙነት ያላቸው መርከቦችን ማገድ እንደሚያካትት ታስኒም የዜና ወኪል ዘግቧል።
ታስኒም የፓርላማ አባል የሆኑትን አባስ ሳሊሚን ጠቅሶ እንደዘገበው የፓርላማው ብሔራዊ ደህንነት እና የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ኮሚቴ በወሽመጡ እና በፐርዢያ ባሕረ ሰላጤ ላይ አገሪቱ የሚኖራትን ቁጥጥር በሚመለከት ተወያይቷል።
በረቂቅ ሕጉ መሠረት አሜሪካ፣ እስራኤል እና ኢራን ጠብ አጫሪ ብላ ከፈረጀቻቸው ሌሎች አገራት ጋር ግንኙነት ያላቸውን መርከቦች በወሽመጡ እንዳያልፉ ይከለከላከሉ።
በረቂቅ ሕጉ በተጨማሪም ከእስራኤል ገር ግንኙነት ያላቸው ወታደራዊ እና የሲቪል የጭነት መርከቦች እንዲሁም በኢራን ላይ በተከፈተው ዘመቻ ድጋፍ ያደረጉ እንዳያልፉ ይከለከላሉ።
በተጨማሪም በኢራን ላይ ጉዳት በማድረስ ረገድ ኃላፊነት አለባቸው ተብለው የሚታመኑ አገራትና ግለሰቦች፣ ካሳ እስኪከፍሉ ድረስ በሆርሙዝ የባሕር ወሽመጥ እና በፋርስ ባሕረ ሰላጤ በኩል የማለፍ ፈቃድ አይሰጣቸውም።
ረቂቅ ሕጉ ለሚፈጸሙ ጥሰቶች ከባድ ቅጣቶችን፤ ከእነዚህም መካከል በመርከብ ላይ የተጫነው ሸቀጥ ካለው ዋጋ እስከ 20 በመቶ የሚደርስ የገንዘብ ቅጣትን አካትቷል።
በሕጉ መሠረት፣ መንግሥት በፋርስ ባህረ ሰላጤ ውስጥ የአሰሳ ስራን ለመቆጣጠር፣ የመርከቦችን እንቅስቃሴ ለመከታተል እንዲሁም ደህንነትን እና የአካባቢ ጥበቃን ለማረጋገጥ ከጦር ኃይሎች ጋር በጋራ እንዲሰራ ይጠበቅበታል።
ሳሊም ሕጉ በባለሙያዎች እየታየ መሆኑን እና ከመጽደቁ በፊት የማሻሻያ ሃሳባቸውን እንዲያቀርቡ ይጠበቃል ብለዋል።
የኢራን ፓርላማ ረቂቅ ሕጉ ላይ የተወያየው አገሪቱ ከኦማን ጋር በወሽመጡ አስተዳደር ላይ እየተነጋገረች ባለችበት እና ከሥምምነት ይደረሳል ተብሎ በሚጠበቅበት ወቅት ነው።
BBC
3 days ago
ከጠቅላይ መሪያችን ጋር መገናኘት አልቻልንም፦ ፔዤሽኪያ
*ፕሬዝዳንቱ በተለያዩ ምክንያቶች ከጠቅላይ መሪያችን ጋር መገናኘት "በጣም አስቸጋሪ" ነው አሉ።
#ethiopia | የኢራኑ ፕሬዝዳንት መስኡድ ፔዜሽኪያን ከሀገሪቱ የበላይ ጠቅላይ መሪ ከሙጅተባ ኻመነኢ ጋር ለመገናኘት አስቸጋሪ መሆኑን ተናገሩ።
የኢራኑ ፕሬዝዳንት መስኡድ ፔዜሽኪያን ከሀገሪቱ የበላይ ጠቅላይ መሪ ከሙጅተባ ኻመነኢ ጋር ግንኙነት ለማድረግና ሀገራዊ ውሳኔዎችን ለማሳለፍ «እጅግ አስቸጋሪ» መሆኑን ይፋ አድርገዋል።
ፕሬዝዳንቱ ይህንን ያሉት ሙጅተባ ኻመነኢ ስልጣን ከያዙ ጀምሮ እስካሁን በአደባባይ ወይም በምስል አለመታየታቸውን ተከተሎ ባለው ከፍተኛ ጥርጣሬ እና ስጋት መካከል ነው።
ፕሬዝዳንት ፔዜሽኪያን ከመንግስት ከፍተኛ አካላት እና ከጠቅላይ መሪው ቢሮ ጋር የሚደረጉ ግንኙነቶች በከፍተኛ የደህንነት ጥበቃ እና በተዘዋዋሪ መንገዶች ብቻ እየተካሄዱ መሆናቸውን ጠቁመዋል።
አዲሱ ጠቅላይ መሪ ሙጅተባ ኻመነኢ ስልጣን ከተረከቡ ወዲህ ምንም አይነት የቀጥታ ስርጭት የቪዲዮ መልዕክት ወይም ህዝባዊ ንግግር አለማድረጋቸው በህዝቡ ዘንድ ጥርጣሬ እንዲፈጠረ አድርጓል ሲል አልጀዚራ ዘግቧል።
ባሁኑ ሰአት በኢራን ከፍተኛ አመራሮች መካከል የመንግስት ውሳኔዎችን በማሳለፍ ረገድ ክፍተቶች እና ውጥረቶች እየተፈጠሩ መሆናቸውን ከቴህራን የሚወጡ ዘገባዎች ያመለክታሉ።
ሔኖክ ወ/ገብርኤል
#ethiopia #getutemesgen #getunews #iran #pezeshkian #supremeleader #mojtabakhamenei #communication
*ፕሬዝዳንቱ በተለያዩ ምክንያቶች ከጠቅላይ መሪያችን ጋር መገናኘት "በጣም አስቸጋሪ" ነው አሉ።
#ethiopia | የኢራኑ ፕሬዝዳንት መስኡድ ፔዜሽኪያን ከሀገሪቱ የበላይ ጠቅላይ መሪ ከሙጅተባ ኻመነኢ ጋር ለመገናኘት አስቸጋሪ መሆኑን ተናገሩ።
የኢራኑ ፕሬዝዳንት መስኡድ ፔዜሽኪያን ከሀገሪቱ የበላይ ጠቅላይ መሪ ከሙጅተባ ኻመነኢ ጋር ግንኙነት ለማድረግና ሀገራዊ ውሳኔዎችን ለማሳለፍ «እጅግ አስቸጋሪ» መሆኑን ይፋ አድርገዋል።
ፕሬዝዳንቱ ይህንን ያሉት ሙጅተባ ኻመነኢ ስልጣን ከያዙ ጀምሮ እስካሁን በአደባባይ ወይም በምስል አለመታየታቸውን ተከተሎ ባለው ከፍተኛ ጥርጣሬ እና ስጋት መካከል ነው።
ፕሬዝዳንት ፔዜሽኪያን ከመንግስት ከፍተኛ አካላት እና ከጠቅላይ መሪው ቢሮ ጋር የሚደረጉ ግንኙነቶች በከፍተኛ የደህንነት ጥበቃ እና በተዘዋዋሪ መንገዶች ብቻ እየተካሄዱ መሆናቸውን ጠቁመዋል።
አዲሱ ጠቅላይ መሪ ሙጅተባ ኻመነኢ ስልጣን ከተረከቡ ወዲህ ምንም አይነት የቀጥታ ስርጭት የቪዲዮ መልዕክት ወይም ህዝባዊ ንግግር አለማድረጋቸው በህዝቡ ዘንድ ጥርጣሬ እንዲፈጠረ አድርጓል ሲል አልጀዚራ ዘግቧል።
ባሁኑ ሰአት በኢራን ከፍተኛ አመራሮች መካከል የመንግስት ውሳኔዎችን በማሳለፍ ረገድ ክፍተቶች እና ውጥረቶች እየተፈጠሩ መሆናቸውን ከቴህራን የሚወጡ ዘገባዎች ያመለክታሉ።
ሔኖክ ወ/ገብርኤል
#ethiopia #getutemesgen #getunews #iran #pezeshkian #supremeleader #mojtabakhamenei #communication
5 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የዩናይትድ ኪንግደም የባህር ንግድ ኦፕሬሽን ማዕከል እንዳስታወቀው፣ ዛሬ [በአካባቢው አቆጣጠር] ማክሰኞ ማለዳ ላይ በኦማን የባህር ዳርቻ አቅራቢያ የምትጓዝ አንዲት የጭነት መርከብ ባልታወቀ ተወንጫፊ መሳሪያ መመታቷን ሪፖርት አድርጋለች። ተቋሙ እንዳብራራው፣ መርከቧ ከኦማኗ ኻሳብ ከተማ በስተሰሜን ምስራቅ 20 የባህር ማይል ርቀት ላይ እየተጓዘች ባለችበት ወቅት ጥቃት እንደደረሰባት በVHF ቻናል 16 የድረሱልኝ ጥሪ አስተላልፋለች።
ይህንን ክስተት ተከትሎ ባለስልጣናት ምርመራ የጀመሩ ሲሆን፣ ዩኬ ኤም ቲ ኦ በቀጠናው የሚያልፉ መርከቦች ከፍተኛ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ እና ማንኛውንም አጠራጣሪ እንቅስቃሴ ለሚመለከተው አካል ሪፖርት እንዲያደርጉ አሳስቧል። እስካሁን ድረስ ለዚህ ጥቃት ኃላፊነት የወሰደ አካል የለም።
ይህ የጥቃት ክስተት የተሰማው፣ በቅርቡ በአሜሪካ እና በኢራን መካከል የተፈጠረውን ወታደራዊ ፍጥጫ ተከትሎ በሆርሙዝ ባህረ ሰላጤ ዙሪያ ውጥረቱ አይሎ ባለበት ወቅት ነው። ዋሽንግተን በዚሁ ስትራቴጂካዊ የውሃ መስመር ላይ የባህር ላይ ጉዞ ነፃነት እንዲረጋገጥ ለቴህራን ጥሪ ስታቀርብ፣ ኢራን በበኩሏ በባህር ዳርቻዎቿ አቅራቢያ የሚደረጉ የመርከብ እንቅስቃሴዎች በእሷ ቁጥጥር እና እይታ ስር መሆን አለባቸው የሚል ጠንካራ አቋም እያንጸባረቀች ትገኛለች።
ባለፈው ቅዳሜ የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በቀጠናው በተደረገ የሽምግልና ጥረት ምክንያት በኢራን ላይ ሊፈጽሙት የነበረውን ወታደራዊ ጥቃት መሰረዛቸውን መግለጻቸው ይታወሳል። ይሁን እንጂ የኢራን ባለስልጣናት ይህን የፕሬዝዳንቱን ንግግር ውድቅ በማድረግ፣ የሆርሙዝ ባህረ ሰላጤን ዳግም ክፍት ለማድረግ የተደረሰ ምንም ዓይነት ስምምነት የለም ሲሉ ሪፖርቶቹን አስተባብለዋል።
ይህንን ክስተት ተከትሎ ባለስልጣናት ምርመራ የጀመሩ ሲሆን፣ ዩኬ ኤም ቲ ኦ በቀጠናው የሚያልፉ መርከቦች ከፍተኛ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ እና ማንኛውንም አጠራጣሪ እንቅስቃሴ ለሚመለከተው አካል ሪፖርት እንዲያደርጉ አሳስቧል። እስካሁን ድረስ ለዚህ ጥቃት ኃላፊነት የወሰደ አካል የለም።
ይህ የጥቃት ክስተት የተሰማው፣ በቅርቡ በአሜሪካ እና በኢራን መካከል የተፈጠረውን ወታደራዊ ፍጥጫ ተከትሎ በሆርሙዝ ባህረ ሰላጤ ዙሪያ ውጥረቱ አይሎ ባለበት ወቅት ነው። ዋሽንግተን በዚሁ ስትራቴጂካዊ የውሃ መስመር ላይ የባህር ላይ ጉዞ ነፃነት እንዲረጋገጥ ለቴህራን ጥሪ ስታቀርብ፣ ኢራን በበኩሏ በባህር ዳርቻዎቿ አቅራቢያ የሚደረጉ የመርከብ እንቅስቃሴዎች በእሷ ቁጥጥር እና እይታ ስር መሆን አለባቸው የሚል ጠንካራ አቋም እያንጸባረቀች ትገኛለች።
ባለፈው ቅዳሜ የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በቀጠናው በተደረገ የሽምግልና ጥረት ምክንያት በኢራን ላይ ሊፈጽሙት የነበረውን ወታደራዊ ጥቃት መሰረዛቸውን መግለጻቸው ይታወሳል። ይሁን እንጂ የኢራን ባለስልጣናት ይህን የፕሬዝዳንቱን ንግግር ውድቅ በማድረግ፣ የሆርሙዝ ባህረ ሰላጤን ዳግም ክፍት ለማድረግ የተደረሰ ምንም ዓይነት ስምምነት የለም ሲሉ ሪፖርቶቹን አስተባብለዋል።
5 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የኢራን አብዮታዊ ዘብ የየብስ ኃይል አዛዥ የሆኑት ሞሀመድ ካራሚ፣ በምዕራብ ኢራን የሚገኙት ታጣቂዎች ከቀጠናው ውጭ ባሉ ጠላቶች ወይም በአሸባሪ ቡድኖች ሊፈጸም ለሚችል ማንኛውም "የተሳሳተ ስሌት" አፋጣኝ ምላሽ ለመስጠት በተጠንቀቅ ላይ እንደሚገኙ ገልጸዋል።
አዛዡ በኤክስ ማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ላይ ባሰፈሩት መልዕክት፣ የሀምዜ ሰይድ አል-ሹሀዳ ዕዝ ታጣቂዎች በስለላ መረጃ፣ በዘመቻ ዝግጁነት እንዲሁም እምነትን፣ ቴክኖሎጂን እና ዘመናዊ ሳይንሶችን በማቀናጀት ለማንኛውም ስጋት ቆራጥ እና የማያዳግም ምላሽ ለመስጠት በተሟላ ዝግጁነት ላይ መሆናቸውን አስታውቀዋል።
ይህ በእንግሊህ እንዳለ የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አባስ አራግቺ እና የኦማን አቻቸው በድር አል-ቡሳይዲ ምሽት ላይ በስልክ ባደረጉት ውይይት በቀጠናው ወቅታዊ የፖለቲካ እና የጸጥታ ጉዳዮች ዙሪያ መምከራቸውን ኢራናዊው ከፍተኛ ዲፕሎማት በቴሌግራም ገጻቸው ይፋ አድርገዋል።
ኦማን እና ኢራን በሁለቱም ሀገራት የውሃ ክልል በሚያዋስነው የሆርሙዝ ስትሬት አዲስ የባህር ላይ መስመር ለመክፈት ድርድር እያደረጉ ይገኛሉ። ይህንን ተከትሎም ባለፈው ምሽት አራግቺ ለኢራን ካቢኔ ባቀረቡት ሪፖርት፣ በቴህራን እና በሙስካት (ኦማን) መካከል እየተካሄደ ያለው ይህ የውሃ መስመር ድርድር "ወደ ማጠናቀቂያው ምዕራፍ እየተቃረበ" መሆኑን አረጋግጠዋል።
አዛዡ በኤክስ ማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ላይ ባሰፈሩት መልዕክት፣ የሀምዜ ሰይድ አል-ሹሀዳ ዕዝ ታጣቂዎች በስለላ መረጃ፣ በዘመቻ ዝግጁነት እንዲሁም እምነትን፣ ቴክኖሎጂን እና ዘመናዊ ሳይንሶችን በማቀናጀት ለማንኛውም ስጋት ቆራጥ እና የማያዳግም ምላሽ ለመስጠት በተሟላ ዝግጁነት ላይ መሆናቸውን አስታውቀዋል።
ይህ በእንግሊህ እንዳለ የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አባስ አራግቺ እና የኦማን አቻቸው በድር አል-ቡሳይዲ ምሽት ላይ በስልክ ባደረጉት ውይይት በቀጠናው ወቅታዊ የፖለቲካ እና የጸጥታ ጉዳዮች ዙሪያ መምከራቸውን ኢራናዊው ከፍተኛ ዲፕሎማት በቴሌግራም ገጻቸው ይፋ አድርገዋል።
ኦማን እና ኢራን በሁለቱም ሀገራት የውሃ ክልል በሚያዋስነው የሆርሙዝ ስትሬት አዲስ የባህር ላይ መስመር ለመክፈት ድርድር እያደረጉ ይገኛሉ። ይህንን ተከትሎም ባለፈው ምሽት አራግቺ ለኢራን ካቢኔ ባቀረቡት ሪፖርት፣ በቴህራን እና በሙስካት (ኦማን) መካከል እየተካሄደ ያለው ይህ የውሃ መስመር ድርድር "ወደ ማጠናቀቂያው ምዕራፍ እየተቃረበ" መሆኑን አረጋግጠዋል።
5 days ago
ኢራን ከአሜሪካ ጋር እየተነጋገርኩ አይደለም አለች
ኢራን ሰኞ ዕለት ከአሜሪካ ጋር ምንም ዓይነት ንግግር እያካሄደች አለመሆኗን ገልጻ፣ ከኦማን ጋር በሆርሙዝ ወሽመጥ ደኅንነቱ የተጠበቀ ጉዞ እንዲደረግ የሚያስችል “ጊዜያዊ የባህር መጓጓዣ መስመር” ለመመስረት እየሰራሁ ነው አለች።
የኢራን ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ እስማኤል ባጋይ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ ቴህራን ከሙስካት ጋር የምታደርገው ንግግር ቁልፍ በሆነው የባሕር መስመር ላይ ጊዜያዊ የመርከቦች መንቀሳቀሻ ለመመስረት ያለመ ነው ብለዋል።
ከኢራን መንግሥት ጋር ቅርበት ያለው ፋርስ የዜና ወኪል እንደዘገበው ባጋይ “ከኦማን ጋር የምናደርገው የአሁኑ ውይይት በሆርሙዝ ባህር ወሽመጥ ውስጥ የመርከቦችን ደኅንነቱ የተጠበቀ ጉዞ ማረጋገጥ ላይ ያተኮረ ነው” ብለዋል።
“በሆርሙዝ ባህር ወሽመጥ ውስጥ የመርከብ ጉዞ ደኅንነትን ለማረጋገጥ እንዲቻል፣ ከኦማን ጋር በመተባበር በተቻለ ፍጥነት ጊዜያዊ የመተላለፊያ መስመር ለመዘርጋት እየሰራን ነው” ሲሉም አክለዋል።
ባጋይ በቴህራን እና በዋሽንግተን መካከል ንግግር እየተደረገ ነው የሚሉ ዘገባዎችን ውድቅ በማድረግ “ከዩናይትድ ስቴትስ ጋር ድርድር እያደረግን አይደለም” ብለዋል።
የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከኢራን ጋር ሰኞ ከሰዓት በኋላ ውይይት እንደሚጀመር ትናንት እሁድ ተናግረው ነበር።
ትራምፕ፣ በሆርሙዝ ጉዳይ እና የኢራንን "ኒውክሌር ማስወገድ" በተመለከተ በቅርቡ ስምምነት ላይ መድረስ እንደሚቻል ያላቸውን ተስፋ ገልጸዋል ።
ባጋይ “አሜሪካ ጥቃቷን እና ክልከላዋን እስከቀጠለች ድረስ [በሆርሙዝ ያለው ሁኔታ ላይ] የሚለወጥ ነገር አይኖርም” ብለዋል።
BBC
ኢራን ሰኞ ዕለት ከአሜሪካ ጋር ምንም ዓይነት ንግግር እያካሄደች አለመሆኗን ገልጻ፣ ከኦማን ጋር በሆርሙዝ ወሽመጥ ደኅንነቱ የተጠበቀ ጉዞ እንዲደረግ የሚያስችል “ጊዜያዊ የባህር መጓጓዣ መስመር” ለመመስረት እየሰራሁ ነው አለች።
የኢራን ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ እስማኤል ባጋይ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ ቴህራን ከሙስካት ጋር የምታደርገው ንግግር ቁልፍ በሆነው የባሕር መስመር ላይ ጊዜያዊ የመርከቦች መንቀሳቀሻ ለመመስረት ያለመ ነው ብለዋል።
ከኢራን መንግሥት ጋር ቅርበት ያለው ፋርስ የዜና ወኪል እንደዘገበው ባጋይ “ከኦማን ጋር የምናደርገው የአሁኑ ውይይት በሆርሙዝ ባህር ወሽመጥ ውስጥ የመርከቦችን ደኅንነቱ የተጠበቀ ጉዞ ማረጋገጥ ላይ ያተኮረ ነው” ብለዋል።
“በሆርሙዝ ባህር ወሽመጥ ውስጥ የመርከብ ጉዞ ደኅንነትን ለማረጋገጥ እንዲቻል፣ ከኦማን ጋር በመተባበር በተቻለ ፍጥነት ጊዜያዊ የመተላለፊያ መስመር ለመዘርጋት እየሰራን ነው” ሲሉም አክለዋል።
ባጋይ በቴህራን እና በዋሽንግተን መካከል ንግግር እየተደረገ ነው የሚሉ ዘገባዎችን ውድቅ በማድረግ “ከዩናይትድ ስቴትስ ጋር ድርድር እያደረግን አይደለም” ብለዋል።
የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከኢራን ጋር ሰኞ ከሰዓት በኋላ ውይይት እንደሚጀመር ትናንት እሁድ ተናግረው ነበር።
ትራምፕ፣ በሆርሙዝ ጉዳይ እና የኢራንን "ኒውክሌር ማስወገድ" በተመለከተ በቅርቡ ስምምነት ላይ መድረስ እንደሚቻል ያላቸውን ተስፋ ገልጸዋል ።
ባጋይ “አሜሪካ ጥቃቷን እና ክልከላዋን እስከቀጠለች ድረስ [በሆርሙዝ ያለው ሁኔታ ላይ] የሚለወጥ ነገር አይኖርም” ብለዋል።
BBC
5 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት ወዲህ የተገመተውን "እጅግ ግዙፍ ጥቃት" በኢራን ላይ ከመፈጸም ማገዳቸውን ተከትሎ፣ ከፊታችን ሰኞ ጀምሮ "በድርድር መልክ" የሚካሄድ አዲስ ውይይት እንደሚጀምሩ አስታውቀዋል። ይሁን እንጂ ኢራን ፕሬዝዳንቱ ለዲፕሎማሲያዊ መፍትሄ ያላቸውን እውነተኛ ቁርጠኝነት በተመለከተ ከፍተኛ ጥርጣሬ አላት።
በኩዊንሲ ኢንስቲትዩት ተመራማሪ የሆኑት ትሪታ ፓርሲ እንደተናገሩት፣ የዲፕሎማሲው ጥረት ስኬታማ እንዲሆን አሜሪካ እና ኢራን ከሆርሙዝ ስትሬት ባሻገር በሌሎች ሰፋፊ ጉዳዮች ላይ ስምምነት ላይ መድረስ አለባቸው።
የሆርሙዝ የውሃ መስመር ጉዳይ አንዱ እና ወሳኙ አካል መሆኑን የጠቀሱት ፓርሲ፣ ባለፈው ሰኔ ወር በአሜሪካ እና በኢራን መካከል የተፈረመው የመግባቢያ ሰነድ በመላው ቀጠናው ተኩስ አቁም እንዲደረግ የሚጠይቅ እንደነበር አስታውሰዋል። ነገር ግን እስራኤል በሊባኖስ እና በጋዛ ላይ የምትፈጽመውን ጥቃት መቀጠሏ የቀጠናውን የተኩስ አቁም ጥያቄ የሚጥስ በመሆኑ፣ ይህ ሰነድ ለታደሰው ዲፕሎማሲ መነሻ የሚሆን ከሆነ "ወደ ነበርንበት አልፎም ወደ ከፋ ሁኔታ ልንመለስ እንችላለን" ሲሉ ሞግተዋል።
ያም ሆኖ ሁለቱም ወገኖች ዲፕሎማሲያዊ ጥረቱ እንዲከሽፍ መፍቀድ እንደሌለባቸው ያስጠነቀቁት ተመራማሪው፣ ምክንያቱም በመጨረሻ የሚኖረው ሌላኛው አማራጭ እጅግ አውዳሚ መሆኑን አስገንዝበዋል።
አክለውም ፕሬዝዳንት ትራምፕ በእርግጥ "ምንም ዓይነት ወታደራዊ አማራጭ እንደሌላቸው" ራሳቸውን እስካላሳመኑ ድረስ ለዘላቂ ስምምነት ይቆማሉ ብላ ቴህራን ስለማታምን፣ ለዲፕሎማሲ ያላቸውን ታማኝነት አሁንም በጥርጣሬ እንደምትመለከተው ፓርሲ አስረድተዋል።
በኩዊንሲ ኢንስቲትዩት ተመራማሪ የሆኑት ትሪታ ፓርሲ እንደተናገሩት፣ የዲፕሎማሲው ጥረት ስኬታማ እንዲሆን አሜሪካ እና ኢራን ከሆርሙዝ ስትሬት ባሻገር በሌሎች ሰፋፊ ጉዳዮች ላይ ስምምነት ላይ መድረስ አለባቸው።
የሆርሙዝ የውሃ መስመር ጉዳይ አንዱ እና ወሳኙ አካል መሆኑን የጠቀሱት ፓርሲ፣ ባለፈው ሰኔ ወር በአሜሪካ እና በኢራን መካከል የተፈረመው የመግባቢያ ሰነድ በመላው ቀጠናው ተኩስ አቁም እንዲደረግ የሚጠይቅ እንደነበር አስታውሰዋል። ነገር ግን እስራኤል በሊባኖስ እና በጋዛ ላይ የምትፈጽመውን ጥቃት መቀጠሏ የቀጠናውን የተኩስ አቁም ጥያቄ የሚጥስ በመሆኑ፣ ይህ ሰነድ ለታደሰው ዲፕሎማሲ መነሻ የሚሆን ከሆነ "ወደ ነበርንበት አልፎም ወደ ከፋ ሁኔታ ልንመለስ እንችላለን" ሲሉ ሞግተዋል።
ያም ሆኖ ሁለቱም ወገኖች ዲፕሎማሲያዊ ጥረቱ እንዲከሽፍ መፍቀድ እንደሌለባቸው ያስጠነቀቁት ተመራማሪው፣ ምክንያቱም በመጨረሻ የሚኖረው ሌላኛው አማራጭ እጅግ አውዳሚ መሆኑን አስገንዝበዋል።
አክለውም ፕሬዝዳንት ትራምፕ በእርግጥ "ምንም ዓይነት ወታደራዊ አማራጭ እንደሌላቸው" ራሳቸውን እስካላሳመኑ ድረስ ለዘላቂ ስምምነት ይቆማሉ ብላ ቴህራን ስለማታምን፣ ለዲፕሎማሲ ያላቸውን ታማኝነት አሁንም በጥርጣሬ እንደምትመለከተው ፓርሲ አስረድተዋል።
6 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ቅዳሜ ምሽት በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልእክት፣ የመካከለኛው ምስራቅ አጋሮች የአምስት ወሩን የኢራን ጦርነት ለማቆም የሚያስችል የስምምነት ማዕቀፍ ላይ መድረሳቸውን ገልጸው፣ ለጊዜው አዲስ ጥቃት ከመሰንዘር እንደሚታቀቡ አስታውቀዋል። ይህ አዲስ ስምምነት የሆርሙዝ የባህር ወሽመጥን በአፋጣኝ እና ሙሉ በሙሉ ክፍት ማድረግን እንዲሁም የኢራንን የኒውክሌር ስጋት ማብቃትን የሚያካትት መሆኑን ፕሬዝዳንቱ አክለዋል። ትራምፕ ለዓለም የወደፊት ጥቅም እንዲሁም ለኢራን ህልውና እና ብልጽግና ስል፣ በፍጥነት ስምምነት ላይ ለመድረስ በማሰብ ጥቃቱን ለመሰረዝ ተስማምቻለሁ ብለዋል። ጦርነቱን የሚያስቆመውን ይህንን ስምምነት ከዳር ለማድረስ በሚደረገው ጥረት፣ እስራኤል ከአሜሪካ ጋር ለመተባበር መስማማቷንም ጠቁመዋል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ፣የሳዑዲ አረቢያው አልጋ ወራሽ እና የሀገሪቱ መሪ ልዑል መሀመድ ቢን ሳልማን ቅዳሜ ዕለት ከትራምፕ ጋር በስልክ በተወያዩበት ወቅት፣ አሜሪካ ከኢራን ጋር ያላትን ግጭት ልታባብስ ትችላለች በሚል ስጋታቸውን ማቅረባቸውን ጉዳዩን በቅርበት የሚያውቁ ምንጮች ገልጸዋል። አክሲዮስ የተሰኘው የዜና አውታር እንደዘገበው፣ ይህ ውይይት የተካሄደው ትራምፕ በኢራን ላይ አዲስ ጥቃት ለመሰንዘር እያመነቱ ባለበት ወቅት ነው። ሳዑዲዎች፣ አሜሪካ የኢራንን የኃይል (ኢነርጂ) መሠረተ ልማቶች ላይ ጥቃት ከሰነዘረች፣ ቴህራን አጸፋውን በሳዑዲ እና በሌሎች የባህረ ሰላጤው ሀገራት የነዳጅ ተቋማት ላይ ልትወጣ ትችላለች የሚል ከፍተኛ ስጋት አድሮባቸዋል። አልጋ ወራሹ በዚህ የስልክ ውይይታቸው፣ ትራምፕ በኢራን ላይ ሊወስዱት ስላሰቡት አዲስ እርምጃ ማብራሪያ ጠይቀዋል። የዋይት ሀውስ ባለስልጣንም የሁለቱን መሪዎች የስልክ ውይይት መካሄድ አረጋግጠዋል።
ሳዑዲ አረቢያ በኢራን ከሚደገፉ የኢራቅ ሚሊሻዎች ጋር በተያያዘ ከአሜሪካ ጋር ወታደራዊ እርምጃዎችን ብትወስድም፣ ግጭቱ በድርድር እንዲፈታ ግፊት እያደረገች ትገኛለች። አልጋ ወራሹም የሳዑዲ መከላከያ ሚኒስትር የሆኑትን ወንድማቸውን ካሊድ ቢን ሳልማንን፣ ስለ ኢራን ስትራቴጂ ከትራምፕ እና ከምክትል ፕሬዝዳንት ጄዲ ቫንስ ጋር እንዲወያዩ ረቡዕ ዕለት ወደ ዋሽንግተን ልከው ነበር። በሌላ በኩል ትራምፕ ባለፈው ማክሰኞ ከእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንጃሚን ኔታንያሁ ጋር በዋይት ሀውስ የተወያዩ ሲሆን፣ የካቲት ወር ላይ ጦርነቱ ከጀመረ ወዲህ በአካል ሲገናኙ ይህ የመጀመሪያቸው ነው። የውይይቱ አካል የነበሩት የእስራኤሉ መሪ ትራምፕ በኢራን ላይ የሚያደርጉትን ጦርነት እንዲቀጥሉ አሳስበዋል።
ይህ የአሜሪካ ወታደራዊ እርምጃ ውጥረት ለትራምፕ እና ለፓርቲያቸው ከፍተኛ ፈተና ሆኗል። በብዙ አሜሪካውያን ዘንድ ተቀባይነት ያጣው ይህ ጦርነት፣ በመጪው ህዳር ወር ከሚካሄደው ወሳኝ የአጋማሽ ዘመን ምርጫ ጥቂት ወራት ቀደም ብሎ የዓለምን ኢኮኖሚ እያናጋው ይገኛል። ፕሬዝዳንቱ ከዚህ ቀደም ኢራን በዮርዳኖስ በሚገኘው የአሜሪካ የጦር ሰፈር ላይ ያደረሰችውን ድንገተኛ ጥቃት ተከትሎ አጸፋዊ እርምጃ እንደሚወስዱ ዝተው ነበር። አርብ ዕለትም አሜሪካ ኢራንን እጅግ አጥብቃ እንደምትመታ ተናግረው ነበር። የዋይት ሀውስ ፕሬዝዳንታዊ ቃል አቀባይ ካሮሊን ሊቪት በበኩላቸው፣ ቴህራን ባለፈው ወር ከአሜሪካ ጋር የተኩስ አቁም ስምምነት ተፈራርማ ወዲያውኑ ስምምነቱን በመጣስ በንግድ መርከቦች ላይ ተኩስ መክፈቷን እና አሜሪካውያን ወታደሮችን መግደሏን አስታውሰዋል።
ይህንኑ ከኢራን ጋር እየተባባሰ የመጣውን ውጥረት ተከትሎ፣ ቅዳሜ ዕለት የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በቀጠናው በሚገኙ 10 ሀገራት ለሚኖሩ አሜሪካውያን አዲስ የደህንነት ማስጠንቀቂያ አውጥቷል። ባሃሬን፣ እስራኤል፣ ኢራቅ፣ ዮርዳኖስ፣ ኩዌት፣ ሊባኖስ፣ ኦማን፣ ኳታር፣ ሳዑዲ አረቢያ እና የተባበሩት አረብ ኤምሬትስን በሚሸፍነው በዚህ ማስጠንቀቂያ፣ የአሜሪካ ዜጎች የበረራ ስረዛዎችን፣ ጊዜያዊ የአየር ክልል መዘጋትን እና ሌሎች የጉዞ መስተጓጎሎችን ታሳቢ በማድረግ ከፍተኛ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ አሳስቧል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ፣የሳዑዲ አረቢያው አልጋ ወራሽ እና የሀገሪቱ መሪ ልዑል መሀመድ ቢን ሳልማን ቅዳሜ ዕለት ከትራምፕ ጋር በስልክ በተወያዩበት ወቅት፣ አሜሪካ ከኢራን ጋር ያላትን ግጭት ልታባብስ ትችላለች በሚል ስጋታቸውን ማቅረባቸውን ጉዳዩን በቅርበት የሚያውቁ ምንጮች ገልጸዋል። አክሲዮስ የተሰኘው የዜና አውታር እንደዘገበው፣ ይህ ውይይት የተካሄደው ትራምፕ በኢራን ላይ አዲስ ጥቃት ለመሰንዘር እያመነቱ ባለበት ወቅት ነው። ሳዑዲዎች፣ አሜሪካ የኢራንን የኃይል (ኢነርጂ) መሠረተ ልማቶች ላይ ጥቃት ከሰነዘረች፣ ቴህራን አጸፋውን በሳዑዲ እና በሌሎች የባህረ ሰላጤው ሀገራት የነዳጅ ተቋማት ላይ ልትወጣ ትችላለች የሚል ከፍተኛ ስጋት አድሮባቸዋል። አልጋ ወራሹ በዚህ የስልክ ውይይታቸው፣ ትራምፕ በኢራን ላይ ሊወስዱት ስላሰቡት አዲስ እርምጃ ማብራሪያ ጠይቀዋል። የዋይት ሀውስ ባለስልጣንም የሁለቱን መሪዎች የስልክ ውይይት መካሄድ አረጋግጠዋል።
ሳዑዲ አረቢያ በኢራን ከሚደገፉ የኢራቅ ሚሊሻዎች ጋር በተያያዘ ከአሜሪካ ጋር ወታደራዊ እርምጃዎችን ብትወስድም፣ ግጭቱ በድርድር እንዲፈታ ግፊት እያደረገች ትገኛለች። አልጋ ወራሹም የሳዑዲ መከላከያ ሚኒስትር የሆኑትን ወንድማቸውን ካሊድ ቢን ሳልማንን፣ ስለ ኢራን ስትራቴጂ ከትራምፕ እና ከምክትል ፕሬዝዳንት ጄዲ ቫንስ ጋር እንዲወያዩ ረቡዕ ዕለት ወደ ዋሽንግተን ልከው ነበር። በሌላ በኩል ትራምፕ ባለፈው ማክሰኞ ከእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንጃሚን ኔታንያሁ ጋር በዋይት ሀውስ የተወያዩ ሲሆን፣ የካቲት ወር ላይ ጦርነቱ ከጀመረ ወዲህ በአካል ሲገናኙ ይህ የመጀመሪያቸው ነው። የውይይቱ አካል የነበሩት የእስራኤሉ መሪ ትራምፕ በኢራን ላይ የሚያደርጉትን ጦርነት እንዲቀጥሉ አሳስበዋል።
ይህ የአሜሪካ ወታደራዊ እርምጃ ውጥረት ለትራምፕ እና ለፓርቲያቸው ከፍተኛ ፈተና ሆኗል። በብዙ አሜሪካውያን ዘንድ ተቀባይነት ያጣው ይህ ጦርነት፣ በመጪው ህዳር ወር ከሚካሄደው ወሳኝ የአጋማሽ ዘመን ምርጫ ጥቂት ወራት ቀደም ብሎ የዓለምን ኢኮኖሚ እያናጋው ይገኛል። ፕሬዝዳንቱ ከዚህ ቀደም ኢራን በዮርዳኖስ በሚገኘው የአሜሪካ የጦር ሰፈር ላይ ያደረሰችውን ድንገተኛ ጥቃት ተከትሎ አጸፋዊ እርምጃ እንደሚወስዱ ዝተው ነበር። አርብ ዕለትም አሜሪካ ኢራንን እጅግ አጥብቃ እንደምትመታ ተናግረው ነበር። የዋይት ሀውስ ፕሬዝዳንታዊ ቃል አቀባይ ካሮሊን ሊቪት በበኩላቸው፣ ቴህራን ባለፈው ወር ከአሜሪካ ጋር የተኩስ አቁም ስምምነት ተፈራርማ ወዲያውኑ ስምምነቱን በመጣስ በንግድ መርከቦች ላይ ተኩስ መክፈቷን እና አሜሪካውያን ወታደሮችን መግደሏን አስታውሰዋል።
ይህንኑ ከኢራን ጋር እየተባባሰ የመጣውን ውጥረት ተከትሎ፣ ቅዳሜ ዕለት የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በቀጠናው በሚገኙ 10 ሀገራት ለሚኖሩ አሜሪካውያን አዲስ የደህንነት ማስጠንቀቂያ አውጥቷል። ባሃሬን፣ እስራኤል፣ ኢራቅ፣ ዮርዳኖስ፣ ኩዌት፣ ሊባኖስ፣ ኦማን፣ ኳታር፣ ሳዑዲ አረቢያ እና የተባበሩት አረብ ኤምሬትስን በሚሸፍነው በዚህ ማስጠንቀቂያ፣ የአሜሪካ ዜጎች የበረራ ስረዛዎችን፣ ጊዜያዊ የአየር ክልል መዘጋትን እና ሌሎች የጉዞ መስተጓጎሎችን ታሳቢ በማድረግ ከፍተኛ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ አሳስቧል።
Sponsored by
Surafel
7 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) ዩናይትድ ስቴትስ እና እስራኤል በኢራን የኃይል መሰረተ ልማቶች ላይ እስካሁን ከተፈጸሙት ሁሉ እጅግ የከፋ የተባለለትን የአየር ድብደባ ለማካሄድ እቅድ ማውጣታቸውን ሲቢኤስ ኒውስ ዘገበ። ጥቃቱ በዚህ የሳምንቱ መጨረሻ ሊፈጸም እንደሚችል በርካታ ምንጮች ጠቁመዋል።
የአየር ድብደባው በአሜሪካ እና በዓለም አቀፉ የኢኮኖሚ ገበያ ላይ ሊያሳድር የሚችለውን ተጽዕኖ በመስጋት፣ ሰኞ የፋይናንስ ገበያዎች ክፍት ከመሆናቸው በፊት ዘመቻውን ለማጠናቀቅ ውይይቶች መደረጋቸው ተገልጿል። ሆኖም የዘመቻው ማብቂያ ጊዜ ገና በግልጽ አልጸደቀም። የአሜሪካ ምንጮች እንዳረጋገጡት፣ ለእስራኤል ማሳወቂያ የተሰጠ ሲሆን ከዩናይትድ ስቴትስ ጋር በቅንጅት እየሰሩ ይገኛሉ። ነገር ግን ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ለጥቃቱ የመጨረሻውን የትዕዛዝ ማረጋገጫ ገና አልሰጡም።
የጥቃቱ እቅድ አርብ ዕለት በካምፕ ዴቪድ በተካሄደው የፕሬዝዳንት ትራምፕ የካቢኔ ስብሰባ ላይ ውይይት የተደረገበት ሲሆን፣ አንዳንድ የዋይት ሀውስ የፖለቲካ አማካሪዎች ሀሳቡን አጥብቀው ቢቃወሙም፤ ትራምፕ በስብሰባው ላይ ለጋዜጠኞች "በጣም በኃይል እንመታቸዋለን። በአንድ ወቅት፣ 'ከዚህ በላይ መቋቋም አንችልም' ማለት ይጀምራሉ" ሲሉ ተደምጠዋል። የኃይል ማመንጫዎችን እና የነዳጅ ማጣሪያዎችን ጨምሮ መሰረተ ልማቶች ዋነኛ ኢላማ ሊሆኑ እንደሚችሉ የተጠቆመ ሲሆን፣ በመላው ቴህራን መብራት ስለማቋረጥ በከፍተኛ ደረጃ ውይይት የተደረገ ቢሆንም እስካሁን የተላለፈ የመጨረሻ ውሳኔ የለም።
የዋይት ሀውስ ፕሬስ ሴክሬታሪ ካሮላይን ሌቪት ለሲቢኤስ ኒውስ በሰጡት መግለጫ፣ ፕሬዝዳንት ትራምፕ በካቢኔ ስብሰባቸው ላይ እንዳሉት፣ አሜሪካ እንደምታሸንፍና በእሳቸው የሥልጣን ዘመንም ኢራን የኒውክሌር ጦር መሣሪያ እንደማይኖራት አረጋግጠዋል። የፔንታጎን ዋና ቃል አቀባይ ሾን ፓርኔል በበኩላቸው፣ ፕሬዝዳንቱ የመጨረሻ ውሳኔ እስኪሰጡ ድረስ ፔንታጎን ስለ ኢላማዎቹ አስተያየት እንደማይሰጥ ገልጸው፣ የጦርነት መምሪያው በማንኛውም ሰዓት የፕሬዝዳንቱን ትዕዛዝ ለመፈጸም ሙሉ ዝግጁነት ላይ መሆኑን አስታውቀዋል። በሌላ በኩል አንድ የእስራኤል ባለስልጣን ለእስራኤል በኢራን ላይ በሚደረግ ወታደራዊ እርምጃ እንድትቀላቀል ጥያቄ እንዳልቀረበላትና ሙሉ ወታደራዊ ዘመቻ ስለመጀመሩ መረጃ እንደሌላት ተናግረዋል።
የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንጃሚን ኔታንያሁ በዚህ ሳምንት መጀመሪያ ላይ ከፕሬዝዳንት ትራምፕ ጋር በተገናኙበት ወቅት፣ የአቅርቦት መስመሮች ላይ ያተኮሩትን ጨምሮ ሦስት የጦርነት አማራጮችን ማቅረባቸው ይታወሳል። ኔታንያሁ ከአሜሪካው የመከላከያ ጸሃፊ ሄግሴት (Hegseth) ጋርም ተወያይተዋል። ፕሬዝዳንት ትራምፕ ባለፈው ሳምንት በሆርሙዝ የባህር ሰርጥ በሚጓዙ መርከቦች ላይ ለሚሰነዘር እያንዳንዱ ጥቃት የኢራንን የኃይል ማመንጫ ወይም ድልድይ አጋያለሁ ሲሉ በ‘ትሩዝ ሶሻል’ (Truth Social) ገጻቸው መጻፋቸው አይዘነጋም። የቀድሞ የአሜሪካ ወታደራዊ ባለስልጣን እንዳብራሩት፣ የኃይል መሰረተ ልማቶችን መምታት የኢራን ጦር አገልግሎት የመስጠት እና አገሪቱን የማስተዳደር አቅም ክፉኛ ያሽመደምደዋል።
የአየር ድብደባው በአሜሪካ እና በዓለም አቀፉ የኢኮኖሚ ገበያ ላይ ሊያሳድር የሚችለውን ተጽዕኖ በመስጋት፣ ሰኞ የፋይናንስ ገበያዎች ክፍት ከመሆናቸው በፊት ዘመቻውን ለማጠናቀቅ ውይይቶች መደረጋቸው ተገልጿል። ሆኖም የዘመቻው ማብቂያ ጊዜ ገና በግልጽ አልጸደቀም። የአሜሪካ ምንጮች እንዳረጋገጡት፣ ለእስራኤል ማሳወቂያ የተሰጠ ሲሆን ከዩናይትድ ስቴትስ ጋር በቅንጅት እየሰሩ ይገኛሉ። ነገር ግን ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ለጥቃቱ የመጨረሻውን የትዕዛዝ ማረጋገጫ ገና አልሰጡም።
የጥቃቱ እቅድ አርብ ዕለት በካምፕ ዴቪድ በተካሄደው የፕሬዝዳንት ትራምፕ የካቢኔ ስብሰባ ላይ ውይይት የተደረገበት ሲሆን፣ አንዳንድ የዋይት ሀውስ የፖለቲካ አማካሪዎች ሀሳቡን አጥብቀው ቢቃወሙም፤ ትራምፕ በስብሰባው ላይ ለጋዜጠኞች "በጣም በኃይል እንመታቸዋለን። በአንድ ወቅት፣ 'ከዚህ በላይ መቋቋም አንችልም' ማለት ይጀምራሉ" ሲሉ ተደምጠዋል። የኃይል ማመንጫዎችን እና የነዳጅ ማጣሪያዎችን ጨምሮ መሰረተ ልማቶች ዋነኛ ኢላማ ሊሆኑ እንደሚችሉ የተጠቆመ ሲሆን፣ በመላው ቴህራን መብራት ስለማቋረጥ በከፍተኛ ደረጃ ውይይት የተደረገ ቢሆንም እስካሁን የተላለፈ የመጨረሻ ውሳኔ የለም።
የዋይት ሀውስ ፕሬስ ሴክሬታሪ ካሮላይን ሌቪት ለሲቢኤስ ኒውስ በሰጡት መግለጫ፣ ፕሬዝዳንት ትራምፕ በካቢኔ ስብሰባቸው ላይ እንዳሉት፣ አሜሪካ እንደምታሸንፍና በእሳቸው የሥልጣን ዘመንም ኢራን የኒውክሌር ጦር መሣሪያ እንደማይኖራት አረጋግጠዋል። የፔንታጎን ዋና ቃል አቀባይ ሾን ፓርኔል በበኩላቸው፣ ፕሬዝዳንቱ የመጨረሻ ውሳኔ እስኪሰጡ ድረስ ፔንታጎን ስለ ኢላማዎቹ አስተያየት እንደማይሰጥ ገልጸው፣ የጦርነት መምሪያው በማንኛውም ሰዓት የፕሬዝዳንቱን ትዕዛዝ ለመፈጸም ሙሉ ዝግጁነት ላይ መሆኑን አስታውቀዋል። በሌላ በኩል አንድ የእስራኤል ባለስልጣን ለእስራኤል በኢራን ላይ በሚደረግ ወታደራዊ እርምጃ እንድትቀላቀል ጥያቄ እንዳልቀረበላትና ሙሉ ወታደራዊ ዘመቻ ስለመጀመሩ መረጃ እንደሌላት ተናግረዋል።
የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንጃሚን ኔታንያሁ በዚህ ሳምንት መጀመሪያ ላይ ከፕሬዝዳንት ትራምፕ ጋር በተገናኙበት ወቅት፣ የአቅርቦት መስመሮች ላይ ያተኮሩትን ጨምሮ ሦስት የጦርነት አማራጮችን ማቅረባቸው ይታወሳል። ኔታንያሁ ከአሜሪካው የመከላከያ ጸሃፊ ሄግሴት (Hegseth) ጋርም ተወያይተዋል። ፕሬዝዳንት ትራምፕ ባለፈው ሳምንት በሆርሙዝ የባህር ሰርጥ በሚጓዙ መርከቦች ላይ ለሚሰነዘር እያንዳንዱ ጥቃት የኢራንን የኃይል ማመንጫ ወይም ድልድይ አጋያለሁ ሲሉ በ‘ትሩዝ ሶሻል’ (Truth Social) ገጻቸው መጻፋቸው አይዘነጋም። የቀድሞ የአሜሪካ ወታደራዊ ባለስልጣን እንዳብራሩት፣ የኃይል መሰረተ ልማቶችን መምታት የኢራን ጦር አገልግሎት የመስጠት እና አገሪቱን የማስተዳደር አቅም ክፉኛ ያሽመደምደዋል።
7 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) ከኢራን ብሔራዊ የደህንነት ምክር ቤት የወጣው አዲስ ማስጠንቀቂያ በቀጠናው ያለውን ወታደራዊ ፍጥጫ ወደ ላቀ ደረጃ አሸጋግሮታል።
ቴህራን ባወጣችው መግለጫ፣ አሜሪካ በደቡባዊ የኢራን ወደቦች ላይ የጣለችውን የባህር ኃይል እገዳ የምትቀጥል ከሆነ፣ በሆርሙዝ የባህር ሰርጥ ላይ ያለው ቁጥጥር ይበልጥ እንደሚጠበቅና ከዚህ በተጨማሪም ሌሎች የባህር መተላለፊያ ሰርጦች ሊዘጉ ወይም ሊቆለፉ እንደሚችሉ ዝታለች።
ኢራን በመግለጫዋ ላይ የሌሎቹን የባህር ሰርጦች ስም በግልጽ ባትጠቅስም፣ ከቴህራን ጋር የጠበቀ ወዳጅነት ያላቸው ሁቲዎች የሚቆጣጠሩት የባቢል መንደብ የባህር ሰርጥ እና የኤደን ባህረ ሰላጤ መሆናቸውን በቀላሉ መረዳት ይቻላል።
የኢራን መንግስት አሜሪካ እገዳውን የምትገፋበት ከሆነ የዓለም አቀፉ የኃይል (የነዳጅ) ገበያ ክፉኛ እንደሚናወጥ አስታውቋል። መግለጫው የአሜሪካ መራጮችንም ጭምር ያነጣጠረ ሲሆን፣ በዓለም አቀፍ የነዳጅ ገበያ ላይ የሚፈጠር ማንኛውም መስተጓጎል በአሜሪካ የአገር ውስጥ የነዳጅ ዋጋ ላይ ቀጥተኛ ተጽዕኖ እንደሚያሳድር የታወቀ ነው።
በዚህም አኳኋን ቴህራን አዲስ የመደራደሪያ እና የማስፈራሪያ እኩልዮሽ በመዘርጋት፣ ለአሜሪካ ማንኛውም እርምጃ የኃይል ምላሽ ለመስጠት የተዘጋጀች ይመስላል።
ይህ የኢራን ማስፈራሪያ የመጣው፣ አሜሪካ እና እስራኤል የኢራንን የኃይል እና የነዳጅ መሰረተ ልማቶች ላይ ጥቃት ለመሰንዘር አዲስ ወታደራዊ ዘመቻ ሊከፍቱ ይችላሉ የሚሉ ግምቶች በበረቱበት ወቅት መሆኑ ዘገባውን ይበልጥ አሳሳቢ አድርጎታል።
ቴህራን ባወጣችው መግለጫ፣ አሜሪካ በደቡባዊ የኢራን ወደቦች ላይ የጣለችውን የባህር ኃይል እገዳ የምትቀጥል ከሆነ፣ በሆርሙዝ የባህር ሰርጥ ላይ ያለው ቁጥጥር ይበልጥ እንደሚጠበቅና ከዚህ በተጨማሪም ሌሎች የባህር መተላለፊያ ሰርጦች ሊዘጉ ወይም ሊቆለፉ እንደሚችሉ ዝታለች።
ኢራን በመግለጫዋ ላይ የሌሎቹን የባህር ሰርጦች ስም በግልጽ ባትጠቅስም፣ ከቴህራን ጋር የጠበቀ ወዳጅነት ያላቸው ሁቲዎች የሚቆጣጠሩት የባቢል መንደብ የባህር ሰርጥ እና የኤደን ባህረ ሰላጤ መሆናቸውን በቀላሉ መረዳት ይቻላል።
የኢራን መንግስት አሜሪካ እገዳውን የምትገፋበት ከሆነ የዓለም አቀፉ የኃይል (የነዳጅ) ገበያ ክፉኛ እንደሚናወጥ አስታውቋል። መግለጫው የአሜሪካ መራጮችንም ጭምር ያነጣጠረ ሲሆን፣ በዓለም አቀፍ የነዳጅ ገበያ ላይ የሚፈጠር ማንኛውም መስተጓጎል በአሜሪካ የአገር ውስጥ የነዳጅ ዋጋ ላይ ቀጥተኛ ተጽዕኖ እንደሚያሳድር የታወቀ ነው።
በዚህም አኳኋን ቴህራን አዲስ የመደራደሪያ እና የማስፈራሪያ እኩልዮሽ በመዘርጋት፣ ለአሜሪካ ማንኛውም እርምጃ የኃይል ምላሽ ለመስጠት የተዘጋጀች ይመስላል።
ይህ የኢራን ማስፈራሪያ የመጣው፣ አሜሪካ እና እስራኤል የኢራንን የኃይል እና የነዳጅ መሰረተ ልማቶች ላይ ጥቃት ለመሰንዘር አዲስ ወታደራዊ ዘመቻ ሊከፍቱ ይችላሉ የሚሉ ግምቶች በበረቱበት ወቅት መሆኑ ዘገባውን ይበልጥ አሳሳቢ አድርጎታል።
8 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አባስ አራግቺ ከእንግሊዙ የውጭ ጉዳይ ጸሃፊ ኤድ ሚሊባንድ ጋር ባደረጉት የስልክ ውይይት፣ እንግሊዝ የኢራንን ኢስላማዊ አብዮታዊ ዘብ እንደ ሀገር አቀፍ ስጋት በመፈረጅ የወሰደችውን ውሳኔ እና አሜሪካና እስራኤል በኢራን ላይ በሚያደርሱት ጥቃት ውስጥ ያላትን ተሳትፎ አጥብቀው አውግዘዋል።
የኢራኑ ታስኒም የዜና ወኪል እንዳዘገበው፣ አራግቺ በቀጠናው ለተፈጠረው አለመረጋጋት ዋነኛ ተጠያቂ ያደረጉት የአሜሪካን እና የእስራኤልን ትንኮሳ ነው። ኢራን በቅን ልቦና ወደ ዲፕሎማሲያዊ መንገድ መግባቷን እና ሰኔ 10 ቀን ጦርነቱን ለማቆም የሚያስችል መግባባት ላይ ደርሳ እንደነበር ያስታወሱት ሚኒስትሩ፣ ሆኖም አሜሪካ ቃሏን በማጠፍ ስምምነቱ እንዳይተገበር ማድረጓን ከሰዋል። በዚህ ሂደት ውስጥ በሶስተኛ ወገኖች የሚፈጠሩ መሰናክሎችም አሁን ያለውን ውስብስብ ሁኔታ ይበልጥ ከማባባስ የዘለለ ፋይዳ እንደሌላቸው አስጠንቅቀዋል።
በተጨማሪም አጥቂ ኃይሎች በሌላ ሀገር ላይ ህገ-ወጥ ጥቃት ለመሰንዘር የአንድን ሀገር ግዛት እና ቁሳቁስ እንዲጠቀሙ መፍቀድ በዓለም አቀፍ ህግ መሰረት እንደ ትንኮሳ የሚቆጠር መሆኑን ሚኒስትሩ አስገንዝበዋል። ይህ ድርጊት ጥቃት የተሰነዘረባት ሀገር (ቴህራን) እራሷን የመከላከል ህጋዊ መብት እንድትጠቀም የሚያስችላት መሆኑንም አራግቺ አጽንኦት ሰጥተዋል።
ሚኒስትሩ ከዚህም ባሻገር ኢራን በሆርሙዝ የባህር ሰርጥ ላይ ያለውን የትራፊክ እንቅስቃሴ ለማስተዳደር ከኦማን ጋር በመተባበር አዲስ አሰራር ለመዘርጋት ያላትን ጽኑ አቋም ገልጸው፣ ሶስተኛ ወገኖች ይህንን ሂደት ከማስተጓጎል እንዲቆጠቡ አሳስበዋል።
ለእነዚህ ክሶች ምላሽ የሰጡት የእንግሊዙ የውጭ ጉዳይ ጸሃፊ ኤድ ሚሊባንድ በበኩላቸው፣ ሀገራቸው በኢራን ላይ እየተካሄደ ባለው ጦርነት ውስጥ ምንም አይነት ተሳትፎ እንደሌላት አብራርተዋል። ሎንዶን በቀጠናው ያለውን ውጥረት በማርገብ ረገድ ለሚደረገው ዲፕሎማሲያዊ መፍትሄ ቁርጠኛ መሆኗንም ጸሃፊው አረጋግጠዋል።
የኢራኑ ታስኒም የዜና ወኪል እንዳዘገበው፣ አራግቺ በቀጠናው ለተፈጠረው አለመረጋጋት ዋነኛ ተጠያቂ ያደረጉት የአሜሪካን እና የእስራኤልን ትንኮሳ ነው። ኢራን በቅን ልቦና ወደ ዲፕሎማሲያዊ መንገድ መግባቷን እና ሰኔ 10 ቀን ጦርነቱን ለማቆም የሚያስችል መግባባት ላይ ደርሳ እንደነበር ያስታወሱት ሚኒስትሩ፣ ሆኖም አሜሪካ ቃሏን በማጠፍ ስምምነቱ እንዳይተገበር ማድረጓን ከሰዋል። በዚህ ሂደት ውስጥ በሶስተኛ ወገኖች የሚፈጠሩ መሰናክሎችም አሁን ያለውን ውስብስብ ሁኔታ ይበልጥ ከማባባስ የዘለለ ፋይዳ እንደሌላቸው አስጠንቅቀዋል።
በተጨማሪም አጥቂ ኃይሎች በሌላ ሀገር ላይ ህገ-ወጥ ጥቃት ለመሰንዘር የአንድን ሀገር ግዛት እና ቁሳቁስ እንዲጠቀሙ መፍቀድ በዓለም አቀፍ ህግ መሰረት እንደ ትንኮሳ የሚቆጠር መሆኑን ሚኒስትሩ አስገንዝበዋል። ይህ ድርጊት ጥቃት የተሰነዘረባት ሀገር (ቴህራን) እራሷን የመከላከል ህጋዊ መብት እንድትጠቀም የሚያስችላት መሆኑንም አራግቺ አጽንኦት ሰጥተዋል።
ሚኒስትሩ ከዚህም ባሻገር ኢራን በሆርሙዝ የባህር ሰርጥ ላይ ያለውን የትራፊክ እንቅስቃሴ ለማስተዳደር ከኦማን ጋር በመተባበር አዲስ አሰራር ለመዘርጋት ያላትን ጽኑ አቋም ገልጸው፣ ሶስተኛ ወገኖች ይህንን ሂደት ከማስተጓጎል እንዲቆጠቡ አሳስበዋል።
ለእነዚህ ክሶች ምላሽ የሰጡት የእንግሊዙ የውጭ ጉዳይ ጸሃፊ ኤድ ሚሊባንድ በበኩላቸው፣ ሀገራቸው በኢራን ላይ እየተካሄደ ባለው ጦርነት ውስጥ ምንም አይነት ተሳትፎ እንደሌላት አብራርተዋል። ሎንዶን በቀጠናው ያለውን ውጥረት በማርገብ ረገድ ለሚደረገው ዲፕሎማሲያዊ መፍትሄ ቁርጠኛ መሆኗንም ጸሃፊው አረጋግጠዋል።
10 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) ሮይተርስ የዜና ወኪል ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸውን ሶስት ምንጮች ጠቅሶ እንደዘገበው፣ ኢራን በሚቀጥሉት ጥቂት ሳምንታት ውስጥ እስከ 400 የሚደርሱ በትከሻ ላይ ተደግፈው የሚተኮሱ የቻይና የአየር መከላከያ ስርዓቶችን የመጀመሪያ ዙር ርክክብ ታደርጋለች ተብሎ ይጠበቃል።
ከ60 እስከ 70 ሚሊዮን ዶላር ይገመታል የተባለው ይህ ግዢ፣ አሜሪካ እና እስራኤል በሀገሪቱ ላይ የከፈቱትን ጦርነት ተከትሎ ቴህራን የአጭር ርቀት የአየር መከላከያ አቅሟን ለማሳደግ የምታደርገው ጉልህ ጥረት አካል መሆኑ ተገልጿል። የተሰነዘሩት ጥቃቶች ኢራን ወሳኝ የሆኑ መሰረተ ልማቶቿን እና ወታደራዊ ሰፈሮቿን ለመጠበቅ ባላት አቅም ላይ ክፍተቶች መኖራቸውን ያጋለጡ ነበሩ።
ሮይተርስ አክሎ እንዳብራራው ከሆነ ውሉ ከ300 እስከ 400 የሚደርሱ በቀላሉ በሰው ሊጓጓዙ የሚችሉ የአየር መከላከያ ስርዓቶችን (MANPADS)፣ በተለይም የቻይናዎቹን QW-12 እና FN-16 ሚሳኤሎችን ግዢ የሚያካትት ነው።
ይህ የግዢ ስምምነት 'ዞንግቺንግ ባኦሻንግ ኢንተርናሽናል ኢንቨስትመንት' ከተባለና ሆንግ ኮንግን መሰረት ካደረገ ተቋም ጋር የተጠናቀቀ ሲሆን፣ ይህ ተቋም የኢራን ባለስልጣናትን ከቻይናው የመከላከያ መሳሪያ አምራች ኩባንያ ጋር በማገናኘት እንደ ደላላ (አማላጅ) ሆኖ ያገለገለ መሆኑን የዜናው ምንጮች አረጋግጠዋል።
ከ60 እስከ 70 ሚሊዮን ዶላር ይገመታል የተባለው ይህ ግዢ፣ አሜሪካ እና እስራኤል በሀገሪቱ ላይ የከፈቱትን ጦርነት ተከትሎ ቴህራን የአጭር ርቀት የአየር መከላከያ አቅሟን ለማሳደግ የምታደርገው ጉልህ ጥረት አካል መሆኑ ተገልጿል። የተሰነዘሩት ጥቃቶች ኢራን ወሳኝ የሆኑ መሰረተ ልማቶቿን እና ወታደራዊ ሰፈሮቿን ለመጠበቅ ባላት አቅም ላይ ክፍተቶች መኖራቸውን ያጋለጡ ነበሩ።
ሮይተርስ አክሎ እንዳብራራው ከሆነ ውሉ ከ300 እስከ 400 የሚደርሱ በቀላሉ በሰው ሊጓጓዙ የሚችሉ የአየር መከላከያ ስርዓቶችን (MANPADS)፣ በተለይም የቻይናዎቹን QW-12 እና FN-16 ሚሳኤሎችን ግዢ የሚያካትት ነው።
ይህ የግዢ ስምምነት 'ዞንግቺንግ ባኦሻንግ ኢንተርናሽናል ኢንቨስትመንት' ከተባለና ሆንግ ኮንግን መሰረት ካደረገ ተቋም ጋር የተጠናቀቀ ሲሆን፣ ይህ ተቋም የኢራን ባለስልጣናትን ከቻይናው የመከላከያ መሳሪያ አምራች ኩባንያ ጋር በማገናኘት እንደ ደላላ (አማላጅ) ሆኖ ያገለገለ መሆኑን የዜናው ምንጮች አረጋግጠዋል።
10 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የአሜሪካ ጦር በኢራን የተተኮሱ በርካታ ሚሳኤሎችን ማክሸፉን ያስታወቀ ሲሆን፣ ይህ ጥቃት በሁለቱ ጠላት ሀገራት መካከል ለቀናት ታይቶ የነበረውን አንጻራዊ መረጋጋት ያቋረጠ ሆኗል።
የአሜሪካ ማዕከላዊ እዝ በኤክስ ማህበራዊ ትስስር ገጹ ላይ ባወጣው መግለጫ፣ "ዛሬ ከቀኑ 11፡45 (በአሜሪካ ምስራቃዊ ሰዓት አቆጣጠር)፣ በመካከለኛው ምስራቅ በሚገኙ የአሜሪካ ኃይሎች ላይ ያልታሰበ ጥቃት ለመሰንዘር በማሰብ የእስላማዊ አብዮታዊ ዘብ ኮር (IRGC) ኃይሎች ከኢራን በርካታ የባሊስቲክ ሚሳኤሎችን ተኩሰዋል" ብሏል። እዙ ኢራን ኢላማ ያደረገችባቸውን የተወሰኑ አካባቢዎች በዝርዝር ባይገልጽም፣
"ሁሉም የኢራን ሚሳኤሎች በተሳካ ሁኔታ ከሽፈዋል" ሲል አክሏል።
አሜሪካ በኢራን ላይ ለሁለት ሳምንታት ገደማ በየምሽቱ ስትሰነዝር የነበረውን ጥቃት፣ እንዲሁም ቴህራን በባህረ ሰላጤው አካባቢ በሚገኙ የዋሽንግተን አጋሮች ላይ በተደጋጋሚ ስትተኩሳቸው የነበሩትን የሚሳኤል እና የድሮን ጥቃቶች ተከትሎ ሁለቱም ወገኖች ባለፈው የሳምንት መጨረሻ ላይ ተኩስ አቁመው ቆይተው ነበር።
በሐምሌ ወር አጋማሽ ላይ ይህ ግጭት እንደገና ሊያገረሽ የቻለው ኢራን በሆርሙዝ የባህር ወሽመጥ በሚገኙ በርካታ መርከቦች ላይ ጥቃት መፈጸሟን ተከትሎ ነው።
በሳምንቱ መጨረሻ ላይ የታየውን አንጻራዊ የውጊያ መረጋጋት፣ እንዲሁም የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ጦርነቱን ለማቆም በሚደረገው ድርድር ላይ መሻሻል ሊታይ የሚችልበት "ጥሩ እድል" አለ ማለታቸውን ተከትሎ የነዳጅ ዋጋ በከፍተኛ ሁኔታ አሽቆልቁሎ ነበር።
የአሜሪካ ማዕከላዊ እዝ በኤክስ ማህበራዊ ትስስር ገጹ ላይ ባወጣው መግለጫ፣ "ዛሬ ከቀኑ 11፡45 (በአሜሪካ ምስራቃዊ ሰዓት አቆጣጠር)፣ በመካከለኛው ምስራቅ በሚገኙ የአሜሪካ ኃይሎች ላይ ያልታሰበ ጥቃት ለመሰንዘር በማሰብ የእስላማዊ አብዮታዊ ዘብ ኮር (IRGC) ኃይሎች ከኢራን በርካታ የባሊስቲክ ሚሳኤሎችን ተኩሰዋል" ብሏል። እዙ ኢራን ኢላማ ያደረገችባቸውን የተወሰኑ አካባቢዎች በዝርዝር ባይገልጽም፣
"ሁሉም የኢራን ሚሳኤሎች በተሳካ ሁኔታ ከሽፈዋል" ሲል አክሏል።
አሜሪካ በኢራን ላይ ለሁለት ሳምንታት ገደማ በየምሽቱ ስትሰነዝር የነበረውን ጥቃት፣ እንዲሁም ቴህራን በባህረ ሰላጤው አካባቢ በሚገኙ የዋሽንግተን አጋሮች ላይ በተደጋጋሚ ስትተኩሳቸው የነበሩትን የሚሳኤል እና የድሮን ጥቃቶች ተከትሎ ሁለቱም ወገኖች ባለፈው የሳምንት መጨረሻ ላይ ተኩስ አቁመው ቆይተው ነበር።
በሐምሌ ወር አጋማሽ ላይ ይህ ግጭት እንደገና ሊያገረሽ የቻለው ኢራን በሆርሙዝ የባህር ወሽመጥ በሚገኙ በርካታ መርከቦች ላይ ጥቃት መፈጸሟን ተከትሎ ነው።
በሳምንቱ መጨረሻ ላይ የታየውን አንጻራዊ የውጊያ መረጋጋት፣ እንዲሁም የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ጦርነቱን ለማቆም በሚደረገው ድርድር ላይ መሻሻል ሊታይ የሚችልበት "ጥሩ እድል" አለ ማለታቸውን ተከትሎ የነዳጅ ዋጋ በከፍተኛ ሁኔታ አሽቆልቁሎ ነበር።
12 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ አሜሪካ ከቴህራን ጋር ውይይት እያደረገች መሆኑን ገልጸው፣ በሂደቱ "መልካም ነገሮች ሊፈጠሩ ይችላሉ" ሲሉ ተናገሩ። ፕሬዝዳንቱ ከኢራን ጋር አዲስ ስምምነት ላይ ለመድረስ ሰፊ ጊዜ እና ብዙ ትዕግስት እንዳላቸውም አረጋግጠዋል።
ኢራን በዋናው የውሃ መስመር ላይ የንግድ መርከቦችን እንቅስቃሴ ለማስተጓጎል በቅርቡ ያደረገችው ሙከራ ቢኖርም፣ የሆርሙዝ የባህር በር ደህንነት "በጣም በጥሩ ሁኔታ" ላይ እንደሚገኝ ትራምፕ ጠቁመዋል። አክለውም ኢራን በአማላጆች በኩል እንዲሁም በቀጥታ ከአሜሪካ ጋር ለመገናኘት ጥያቄ ማቅረቧን አብራርተዋል።
በወቅቱ አንድ ጋዜጠኛ ለነገሮች ምን ያህል ትዕግስት እንዳላቸው ላቀረበላቸው ጥያቄ ሲመልሱ፣ "ብዙ ትዕግስት አለኝ፤ በቂ ጊዜም አለኝ" ብለዋል። በሁለቱ ሀገራት መካከል አሁን ላይ "ጥሩ ውይይቶች" እየተደረጉ መሆኑን ያነሱት ፕሬዝዳንቱ፤ "አንድ ነገር ሊፈጠር የሚችልበት ጥሩ አጋጣሚ አለ ብዬ አስባለሁ። ከተሳካ ጥሩ ነው፤ ካልተሳካ ደግሞ ከሁለት ቀናት በፊት ወደምናደርገው ነገር እንመለሳለን" በማለት አቋማቸውን አንጸባርቀዋል።
ኢራን በዋናው የውሃ መስመር ላይ የንግድ መርከቦችን እንቅስቃሴ ለማስተጓጎል በቅርቡ ያደረገችው ሙከራ ቢኖርም፣ የሆርሙዝ የባህር በር ደህንነት "በጣም በጥሩ ሁኔታ" ላይ እንደሚገኝ ትራምፕ ጠቁመዋል። አክለውም ኢራን በአማላጆች በኩል እንዲሁም በቀጥታ ከአሜሪካ ጋር ለመገናኘት ጥያቄ ማቅረቧን አብራርተዋል።
በወቅቱ አንድ ጋዜጠኛ ለነገሮች ምን ያህል ትዕግስት እንዳላቸው ላቀረበላቸው ጥያቄ ሲመልሱ፣ "ብዙ ትዕግስት አለኝ፤ በቂ ጊዜም አለኝ" ብለዋል። በሁለቱ ሀገራት መካከል አሁን ላይ "ጥሩ ውይይቶች" እየተደረጉ መሆኑን ያነሱት ፕሬዝዳንቱ፤ "አንድ ነገር ሊፈጠር የሚችልበት ጥሩ አጋጣሚ አለ ብዬ አስባለሁ። ከተሳካ ጥሩ ነው፤ ካልተሳካ ደግሞ ከሁለት ቀናት በፊት ወደምናደርገው ነገር እንመለሳለን" በማለት አቋማቸውን አንጸባርቀዋል።
Sponsored by
Surafel
17 days ago
አሜሪካ በኢራን ላይ የምታካሂደውን ጥቃት አጠናክራ ቀጥላለች
አሜሪካ ለ11ኛ ተከታታይ ምሽት በኢራን ላይ የአየር ጥቃት የሰነዘረች ሲሆን፥ቴህራን በበኩሏ ዋሽንግተን በኑክሌር ተቋማቷ ላይ ከሚሰነዘር ጥቃት እንድትቆጠብ አጥብቃ አስጠንቅቃለች።
የአሜሪካ ማዕከላዊ ዕዝ እንደገለጸው፥የተሰነዘረው የጥቃት ማዕበል “ኢራን በሆርሙዝ የባህር ወሽመጥ በሚያልፉ የንግድ መርከቦች ላይ የምታደርሰውን ዛቻ የመቀነስ” አላማ ያለው ነው።
የኢራን መንግስት መገናኛ ብዙሃን በዋና ከተማዋ ቴህራን የአየር መከላከያ ስርአቶች መስራታቸውን ዘግበዋል።
በተጨማሪም በታብሪዝ፣ ቻባሃር፣ ኮናራክ እና የሀገሪቱ ብቸኛ የኑክሌር ሀይል ማመንጫ በሚገኝበት ቡሼህር ከተሞች የፍንዳታ ድምፆች ተሰምተዋል።
ዶናልድ ትራምፕ አሜሪካ በናታንዝ አቅራቢያ የሚገኘውን የመሬት ውስጥ የኑክሌር ተቋም በቅርቡ እንደምትመታ ከተናገሩ በኋላ፤ የበቀል እርምጃ እንደምትወስድ ያስጠነቀቀችው ኢራን በአሜሪካ እና በመካከለኛው ምስራቅ ወዳጆቿ ላይ አጸፋዊ ጥቃት እንደምትሰነዝር ገልጻለች።
Seledadotio
Seledadotio
አሜሪካ ለ11ኛ ተከታታይ ምሽት በኢራን ላይ የአየር ጥቃት የሰነዘረች ሲሆን፥ቴህራን በበኩሏ ዋሽንግተን በኑክሌር ተቋማቷ ላይ ከሚሰነዘር ጥቃት እንድትቆጠብ አጥብቃ አስጠንቅቃለች።
የአሜሪካ ማዕከላዊ ዕዝ እንደገለጸው፥የተሰነዘረው የጥቃት ማዕበል “ኢራን በሆርሙዝ የባህር ወሽመጥ በሚያልፉ የንግድ መርከቦች ላይ የምታደርሰውን ዛቻ የመቀነስ” አላማ ያለው ነው።
የኢራን መንግስት መገናኛ ብዙሃን በዋና ከተማዋ ቴህራን የአየር መከላከያ ስርአቶች መስራታቸውን ዘግበዋል።
በተጨማሪም በታብሪዝ፣ ቻባሃር፣ ኮናራክ እና የሀገሪቱ ብቸኛ የኑክሌር ሀይል ማመንጫ በሚገኝበት ቡሼህር ከተሞች የፍንዳታ ድምፆች ተሰምተዋል።
ዶናልድ ትራምፕ አሜሪካ በናታንዝ አቅራቢያ የሚገኘውን የመሬት ውስጥ የኑክሌር ተቋም በቅርቡ እንደምትመታ ከተናገሩ በኋላ፤ የበቀል እርምጃ እንደምትወስድ ያስጠነቀቀችው ኢራን በአሜሪካ እና በመካከለኛው ምስራቅ ወዳጆቿ ላይ አጸፋዊ ጥቃት እንደምትሰነዝር ገልጻለች።
Seledadotio
Seledadotio
17 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የአሜሪካው ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ በፊሊፒንስ ዋና ከተማ ማኒላ በተካሄደው የደቡብ ምሥራቅ እስያ መንግሥታት ማኅበር (አሴአን) ስብሰባ ላይ እንደገለጹት፣ ዋሽንግተን ከኢራን ጋር ያሉባትን ልዩነቶች በድርድር ለመፍታትና ዲፕሎማሲያዊ መንገዶችን ለመከተል አሁንም ዝግጁ ነች። ሚኒስትሩ ኢራን በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ መንገድ ከዋሽንግተን ጋር የመነጋገር ፍላጎት እንዳላት የሚጠቁሙ ግንኙነቶችን እያደረገች መሆኑን የጠቀሱ ቢሆንም፣ አሁን ያለው ዋናው ችግር ግን ቴህራን ለንግግሩ እውነተኛ ቁርጠኝነትና ፍላጎት ማጣቷ ነው ሲሉ ወቅሰዋል።
ሩቢዮ አክለውም ኢራን ለድርድር እውነተኛ ከሆነች አሜሪካም እውነተኛ እንደምትሆን፣ ካልሆነ ግን የአሜሪካንና የሕዝቦቿን እንዲሁም የአጋሮቿን ጥቅም ለማስጠበቅ አስፈላጊውን እርምጃ ሁሉ ለመውሰድ እንደማታቅማማና የገቡትን ቃል ካላከበሩ ከባድ መዘዝ እንደሚከተል አስጠንቅቀዋል። በሌላ በኩል ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ዋሽንግተን ኢራን ትርጉም ላለው ድርድር ዝግጁ እስካልሆነች ድረስ የመገናኘት ምንም ዓይነት ፍላጎት እንደሌላት የገለጹ ሲሆን፣ ኢራን የኑክሌር ሴንትሪፊውጆቿን ወደ ፒክአክስ ተራራ ስላዛወረችበት ወሬ አሜሪካ በእጇ ላይ ያለው ይፋዊ መረጃ ባይኖርም፣ ያ ስፍራ ግን በቅርቡና በጣም በከባድ ሁኔታ እንደሚመታ በድጋሚ ዝተዋል።
ይህ የዋሽንግተን ዲፕሎማሲያዊና ወታደራዊ መግለጫ፣ የትራምፕ አስተዳደር በኢራን ላይ የከረረ ወታደራዊ ጫናን እና የዲፕሎማሲያዊ ማግባባትን ባለሁለት ገጽታ ስልት በጋራ እያራመደ መሆኑን ያሳያል። ውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ በአሴአን መድረክ ላይ ሆነው አሜሪካ ሁልጊዜም ለዲፕሎማሲ ዝግጁ ነች ማለታቸው፣ በዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ዘንድ ዋሽንግተን የጦርነት አጫሪ እንዳትመስልና በቀጠናው የሚገኙ አጋሮቿን የዲፕሎማሲ ድጋፍ ለማሰባሰብ የታለመ ስልታዊ እርምጃ ነው።
በተቃራኒው ግን ፕሬዝዳንት ትራምፕ ቴህራን ትርጉም ላለው ድርድር እስካልቀረበች ድረስ የመገናኘት ፍላጎት የለኝም ማለታቸውና የኑክሌር ጣቢያውን በከባድ ሁኔታ እመታዋለሁ ብለው በድጋሚ መዛታቸው፣ ኢራን በኩዌት የአሜሪካ ጦር ሰፈር ላይ ከፈጸመችው የድሮን ጥቃት እና ከቅርብ ጊዜው የጦርነት መባባስ በኋላ አሜሪካ ደካማ ሆና እንዳትታይና በቴህራን ላይ የበላይነቱን ለመያዝ የምታደርገውን የስነ-ልቦና ጦርነት ያሳያል።
ትራምፕ አሜሪካ ኢራን ሴንትሪፊውጆችን ወደ ፒክአክስ ተራራ ስለማዛወሯ መረጃ የላትም ማለታቸው ቀደም ሲል ይናፈሱ የነበሩ ወታደራዊ የደኅንነት ወሬዎችን የሚያረቅስ ቢሆንም፣ ጥቃቱ ግን በማንኛውም ሰዓት ሊፈጸም እንደሚችል መግለጻቸው ቀውሱን ይበልጥ አሳሳቢ ያደርገዋል።
ይህ የዋሽንግተን “እውነተኛ ካልሆናችሁ እርምጃ እንወስዳለን” የሚለው ጠንካራ አቋም፣ የዲፕሎማሲው በር መከፈት በኢራን በኩል ሙሉ በሙሉ እጅ መስጠትንና የአሜሪካን ቅድመ-ሁኔታዎች መቀበልን ብቻ ታሳቢ ያደረገ መሆኑን ያመላክታል። ስለሆነም የሁለቱ ሀገራት ድብቅና ይፋዊ ግንኙነቶች በፍጥነት ወደ ተጨባጭ የጠረጴዛ ዙሪያ ድርድር ካልተቀየሩ፣ የቃላት ፍልሚያውና መሬት ላይ ያለው የወታደራዊ ተቋማት የሃይል ልውውጥ መላውን መካከለኛው ምስራቅ ወደማይወጡበት መጠነ-ሰፊ ቀጠናዊ ጦርነት ሊከተው እንደሚችል ዓለም አቀፍ የዲፕሎማሲ ተንታኞች በጥብቅ ያስገነዝባሉ።
ሩቢዮ አክለውም ኢራን ለድርድር እውነተኛ ከሆነች አሜሪካም እውነተኛ እንደምትሆን፣ ካልሆነ ግን የአሜሪካንና የሕዝቦቿን እንዲሁም የአጋሮቿን ጥቅም ለማስጠበቅ አስፈላጊውን እርምጃ ሁሉ ለመውሰድ እንደማታቅማማና የገቡትን ቃል ካላከበሩ ከባድ መዘዝ እንደሚከተል አስጠንቅቀዋል። በሌላ በኩል ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ዋሽንግተን ኢራን ትርጉም ላለው ድርድር ዝግጁ እስካልሆነች ድረስ የመገናኘት ምንም ዓይነት ፍላጎት እንደሌላት የገለጹ ሲሆን፣ ኢራን የኑክሌር ሴንትሪፊውጆቿን ወደ ፒክአክስ ተራራ ስላዛወረችበት ወሬ አሜሪካ በእጇ ላይ ያለው ይፋዊ መረጃ ባይኖርም፣ ያ ስፍራ ግን በቅርቡና በጣም በከባድ ሁኔታ እንደሚመታ በድጋሚ ዝተዋል።
ይህ የዋሽንግተን ዲፕሎማሲያዊና ወታደራዊ መግለጫ፣ የትራምፕ አስተዳደር በኢራን ላይ የከረረ ወታደራዊ ጫናን እና የዲፕሎማሲያዊ ማግባባትን ባለሁለት ገጽታ ስልት በጋራ እያራመደ መሆኑን ያሳያል። ውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ በአሴአን መድረክ ላይ ሆነው አሜሪካ ሁልጊዜም ለዲፕሎማሲ ዝግጁ ነች ማለታቸው፣ በዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ዘንድ ዋሽንግተን የጦርነት አጫሪ እንዳትመስልና በቀጠናው የሚገኙ አጋሮቿን የዲፕሎማሲ ድጋፍ ለማሰባሰብ የታለመ ስልታዊ እርምጃ ነው።
በተቃራኒው ግን ፕሬዝዳንት ትራምፕ ቴህራን ትርጉም ላለው ድርድር እስካልቀረበች ድረስ የመገናኘት ፍላጎት የለኝም ማለታቸውና የኑክሌር ጣቢያውን በከባድ ሁኔታ እመታዋለሁ ብለው በድጋሚ መዛታቸው፣ ኢራን በኩዌት የአሜሪካ ጦር ሰፈር ላይ ከፈጸመችው የድሮን ጥቃት እና ከቅርብ ጊዜው የጦርነት መባባስ በኋላ አሜሪካ ደካማ ሆና እንዳትታይና በቴህራን ላይ የበላይነቱን ለመያዝ የምታደርገውን የስነ-ልቦና ጦርነት ያሳያል።
ትራምፕ አሜሪካ ኢራን ሴንትሪፊውጆችን ወደ ፒክአክስ ተራራ ስለማዛወሯ መረጃ የላትም ማለታቸው ቀደም ሲል ይናፈሱ የነበሩ ወታደራዊ የደኅንነት ወሬዎችን የሚያረቅስ ቢሆንም፣ ጥቃቱ ግን በማንኛውም ሰዓት ሊፈጸም እንደሚችል መግለጻቸው ቀውሱን ይበልጥ አሳሳቢ ያደርገዋል።
ይህ የዋሽንግተን “እውነተኛ ካልሆናችሁ እርምጃ እንወስዳለን” የሚለው ጠንካራ አቋም፣ የዲፕሎማሲው በር መከፈት በኢራን በኩል ሙሉ በሙሉ እጅ መስጠትንና የአሜሪካን ቅድመ-ሁኔታዎች መቀበልን ብቻ ታሳቢ ያደረገ መሆኑን ያመላክታል። ስለሆነም የሁለቱ ሀገራት ድብቅና ይፋዊ ግንኙነቶች በፍጥነት ወደ ተጨባጭ የጠረጴዛ ዙሪያ ድርድር ካልተቀየሩ፣ የቃላት ፍልሚያውና መሬት ላይ ያለው የወታደራዊ ተቋማት የሃይል ልውውጥ መላውን መካከለኛው ምስራቅ ወደማይወጡበት መጠነ-ሰፊ ቀጠናዊ ጦርነት ሊከተው እንደሚችል ዓለም አቀፍ የዲፕሎማሲ ተንታኞች በጥብቅ ያስገነዝባሉ።
19 days ago
ዓለምን ዳግም ወደ ስጋት የከተተው የቴህራን እና ዋሽንግተን ወታደራዊ ግጭት
**********************
ባለፈው ወር በፓኪስታን አጋዥነት የተደረሰው የጋራ መግባቢያ ስምምነት ሙሉ በሙሉ መፍረሱን ተከትሎ፣ በሁለቱ ኃይላት መካከል ለቀናት የቀጠለው ጥቃት የቀጣናውን የጸጥታና የዓለም አቀፍ የነዳጅ ንግድ መስመር ከባድ ሥጋት ላይ ጥሎታል።
አሁን ላይ ዓለም አቀፍ ሕግጋትን ወደ መጣስ እና የኒውክሌር ተቋማትን ወደ ማጥቃት የተሸጋገረው ይህ አደገኛ ምዕራፍ፣ መላውን ዓለም ወደማይወጣበት ሁለንተናዊ ቀውስ ሊከተው የሚችል አሳሳቢ ደረጃ ላይ ደርሷል።
የግጭቱ መነሻ የአሜሪካ ማዕከላዊ ዕዝ (CENTCOM) ይፋ ባደረገው መግለጫ መሠረት፣ በዮርዳኖስ በሚገኝ ወታደራዊ የጦር ሰፈር ላይ በተሰነዘረ የሰው አልባ አውሮፕላን ጥቃት ሁለት የአሜሪካ ወታደሮች መገደላቸውንና ወታደራዊ ተሽከርካሪዎች መውደማቸውን ተከትሎ የተከሰተ ነው።
ዋሽንግተን ለዚህ አጸፋዊ ምላሽ ይሆን ዘንድ በደቡባዊና ደቡብ ምዕራብ ኢራን በሚገኘው የዳርክሆቨይን የኒውክሌር ኃይል ማመንጫ ግንባታ ቦታ ላይ ሳይቀር ያነጣጠረ የሚሳኤል ጥቃት ፈጽማለች።
ፔንታገን ጥቃቱን በቀጥታ ከማረጋገጥም ሆነ ከመካድ የተቆጠበ ቢሆንም፣ "አሜሪካ ወታደሮቿን ከጥቃት ለመከላከልና የኢራንን የማጥቃት አቅም ለማዳከም ማንኛውንም እርምጃ ትወስዳለች" ሲል ድርጊቱን በተዘዋዋሪ ተከላክሏል፤ ጥቃቶቹም በዋናነት የኢራንን ወታደራዊ የሎጅስቲክስ መሠረተ-ልማቶች ላይ ያነጣጠሩ መሆቸውን ትሟገታለች።
ይሁን እንጂ የኢራን የአቶሚክ ኢነርጂ ድርጅት ጥቃቱን "የሀገሪቱን የሳይንስ ዕድገትና ነጻነት ለማደናቀፍ የታለመ አረመኔያዊ የሽብር ድርጊት" ሲል በጽኑ ኮንኖታል።
ቴህራን ተቋሙ ሙሉ በሙሉ ለዓለም አቀፉ የአቶሚክ ኢነርጂ ኤጀንሲ የደኅንነት ጥበቃ ሥርዓት ተገዢና ሰላማዊ መሆኑን በመጥቀስ፣ አሜሪካ ዓለም አቀፍ ሕግን በግልጽ መጣሷን አስታውቃለች።
በአሜሪካ የአየር ጥቃቶች ሳቢያ እስካሁን በኢራን ቢያንስ 50 ሰዎች መገደላቸውንና ከ500 በላይ መቁሰላቸውን የገለጸው የሀገሪቱ ጤና ሚኒስቴር፣ በርካታ ድልድዮችና ሲቪል መሠረተ-ልማቶች መውደማቸውን አረጋግጧል።
ለአሜሪካ ጥቃት የኢራን ወታደራዊ ምላሽ ፈጣንና መጠነ-ሰፊ የነበረ ሲሆን፣ የኢራን እስላማዊ አብዮታዊ ጥበቃ ኃይል "ናስር-2" የተሰኘውንና 20ኛ ምዕራፍ ላይ የደረሰውን የሚሳኤልና የድሮን ጥቃት የሰነዘረ ሲሆን፣ የኢራን መደበኛ ጦር በበኩሉ "ሳዕቃ" የተሰኘውን 15ኛ ምዕራፍ የጥቃት ዘመቻ አካሂዷል።
በጥቃቶቹ በኩዌት የሚገኘው አሊ አል-ሳሌም የአየር ኃይል ሰፈር፣ ካምፕ አሪፍጃን፣ ካምፕ አዳይሪ እና ሚና አብዱላህ የተሰኘው የሎጂስቲክስ ማዕከል በከባድ ሁኔታ ተመተዋል።
ከዚህም በተጨማሪ፣ በባህሬን የሚገኘው የአሜሪካ አምስተኛ ፍሊት ዋና መሥሪያ ቤት እና በዮርዳኖስ በሚገኘው አል-አዝራቅ የአየር ኃይል ሰፈር ላይ ጥቃት ተፈጽሟል። ምንም እንኳ የአሜሪካ እና የባሕረ-ሰላጤው አገራት መከላከያ ተቋማት አብዛኞቹን የኢራን ሚሳኤሎችና ድሮኖች ማክሸፋቸውን በይፋ ቢገልጹም፣ የወጡ የሳተላይት ምስሎች ግን የተለየ እውነታ እያሳዩ ነው።
የዋሽንግተን ፖስት የምርመራ ሪፖርት እንደሚያመለክተው፣ በክልሉ በሚገኙ 15 የአሜሪካ ወታደራዊ ይዞታዎች ውስጥ የራዳር ሥርዓቶች፣ የፓትሪዮት መከላከያ መሣሪያዎች እና የመጋዘን ተቋማትን ጨምሮ 228 መዋቅሮች በከፊልም ሆነ በሙሉ መውደማቸውን አረጋግጧል።
ይህ ወታደራዊ መካረር በዓለም አቀፍ ዲፕሎማሲና ኢኮኖሚ ላይ ከፍተኛ መናወጥን አስከትሏል። የኢራንን ይፋዊ አቤቱታ ተከትሎ፣ የዓለም አቀፉ አቶሚክ ኢነርጂ ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር ባወጡት መግለጫ፣ በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ጠቅላላ ጉባኤ ውሳኔዎች ቁጥር 444 እና 533 መሠረት፣ በሰላማዊ የኒውክሌር ተቋማት ላይ የሚሰነዘር ማንኛውም ጥቃት ዓለም አቀፍ ሕግን የሚጥስ መሆኑን አስታውሰዋል።
የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሐፊ በበኩላቸው፣ የኒውክሌር ተቋማትን ኢላማ ማድረግ የቀጣናውን ውጥረት ወደማይመለስ አደገኛ አደጋ ሊቀይረው እንደሚችል አስጠንቅቀው፣ የጸጥታው ምክር ቤት በአስቸኳይ እንዲመክርና ሁለቱም ወገኖች ራስን የመግታት እርምጃ እንዲወስዱ ጥሪ አቅርበዋል።
"የኒውክሌር መሠረተ-ልማቶችን ማጥቃት ቀጣናውን ብቻ ሳይሆን መላውን ዓለም ወደማይወጣበት ሁለንተናዊ ቀውስ ውስጥ የሚከት አደገኛ ድርጊት ነው" የሚለው የሰላም ጥሪ መግለጫ የሁኔታውን አሳሳቢነት በግልጽ ያሳያል።
በፖለቲካው ረገድ የሁለቱ ሀገራት መሪዎች የቃላት መለዋወጥ ይበልጥ ጠንክሯል። የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ዋሽንግተን በኩዌትና ባህሬን ላሉት የጦር ሰፈሮቿ ተጨማሪ የአየር መከላከያ ዘዴዎችን በፍጥነት ለማስፈር እያቀደች መሆኑን የገለጹ ሲሆን፣ ኢራን የኒውክሌር ታጣቂ እንድትሆን ፈጽሞ እንደማይፈቅዱ ተናግረዋል።
በሌላ በኩል፣ የኢራን መንፈሣዊ መሪ ሞጅታባ ኻሜኒ እና የፓርላማው አፈ-ጉባኤ መሀመድ ባቄር ቃሊባፍ፣ ዋሽንግተን ስምምነቱን በተጠቀሰው መሠረት ደጋግማ መጣሷ የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ፊርማ ፍጹም ዋጋ ቢስ መሆኑን ያረጋገጠ ነው ብለዋል። የሀገሪቱን ደኅንነት ለማረጋገጥ መላው የኢራን ሕዝብ ቅዱስ ያሉት "አንድነት" እንዲኖረው ጥሪ አቅርበዋል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ ዋሽንግተን በኢራን ወደቦች ላይ የባሕር እገዳ ለመጣል መሞከሯን ተከትሎ፣ ቴህራን በበኩሏ የዓለም የነዳጅ ንግድ ወሳኝ የደም ሥር የሆነውን የሆርሙዝ ሰርጥ ሙሉ በሙሉ ዝግ መሆኑን አውጃለች።
ይህንን የባሕረ-ሰላጤው መዘጋት ተከትሎ፣ የዓለም የነዳጅ ዋጋ (Brent Crude) በአንድ ጀምበር ከፍተኛ የዋጋ ጭማሪ አሳይቷል።
ዓለም አቀፍ የኢነርጂ ተንታኞች ውጥረቱ በዚህ የሚቀጥል ከሆነ በተለይ በእስያ እና በአውሮፓ አገራት ላይ ከባድ የነዳጅ እጥረትና የዋጋ ግሽበት ሊከሰት እንደሚችልና የንግድ መርከቦች ረጅም ርቀት ወደሚጠይቀው የአፍሪካ አቅጣጫ መስመራቸውን ለመቀየር እየተገደዱ መሆኑን እየገለጹ ይገኛሉ።
ፍጥጫው ወታደራዊ ጡንቻን ከማሳየት አልፎ የዓለምን መደበኛ የኢኮኖሚና የጸጥታ መዋቅር የቀየረ ታሪካዊ ቀውስ ሆኗል።
በሰለሞን ገዳ
**********************
ባለፈው ወር በፓኪስታን አጋዥነት የተደረሰው የጋራ መግባቢያ ስምምነት ሙሉ በሙሉ መፍረሱን ተከትሎ፣ በሁለቱ ኃይላት መካከል ለቀናት የቀጠለው ጥቃት የቀጣናውን የጸጥታና የዓለም አቀፍ የነዳጅ ንግድ መስመር ከባድ ሥጋት ላይ ጥሎታል።
አሁን ላይ ዓለም አቀፍ ሕግጋትን ወደ መጣስ እና የኒውክሌር ተቋማትን ወደ ማጥቃት የተሸጋገረው ይህ አደገኛ ምዕራፍ፣ መላውን ዓለም ወደማይወጣበት ሁለንተናዊ ቀውስ ሊከተው የሚችል አሳሳቢ ደረጃ ላይ ደርሷል።
የግጭቱ መነሻ የአሜሪካ ማዕከላዊ ዕዝ (CENTCOM) ይፋ ባደረገው መግለጫ መሠረት፣ በዮርዳኖስ በሚገኝ ወታደራዊ የጦር ሰፈር ላይ በተሰነዘረ የሰው አልባ አውሮፕላን ጥቃት ሁለት የአሜሪካ ወታደሮች መገደላቸውንና ወታደራዊ ተሽከርካሪዎች መውደማቸውን ተከትሎ የተከሰተ ነው።
ዋሽንግተን ለዚህ አጸፋዊ ምላሽ ይሆን ዘንድ በደቡባዊና ደቡብ ምዕራብ ኢራን በሚገኘው የዳርክሆቨይን የኒውክሌር ኃይል ማመንጫ ግንባታ ቦታ ላይ ሳይቀር ያነጣጠረ የሚሳኤል ጥቃት ፈጽማለች።
ፔንታገን ጥቃቱን በቀጥታ ከማረጋገጥም ሆነ ከመካድ የተቆጠበ ቢሆንም፣ "አሜሪካ ወታደሮቿን ከጥቃት ለመከላከልና የኢራንን የማጥቃት አቅም ለማዳከም ማንኛውንም እርምጃ ትወስዳለች" ሲል ድርጊቱን በተዘዋዋሪ ተከላክሏል፤ ጥቃቶቹም በዋናነት የኢራንን ወታደራዊ የሎጅስቲክስ መሠረተ-ልማቶች ላይ ያነጣጠሩ መሆቸውን ትሟገታለች።
ይሁን እንጂ የኢራን የአቶሚክ ኢነርጂ ድርጅት ጥቃቱን "የሀገሪቱን የሳይንስ ዕድገትና ነጻነት ለማደናቀፍ የታለመ አረመኔያዊ የሽብር ድርጊት" ሲል በጽኑ ኮንኖታል።
ቴህራን ተቋሙ ሙሉ በሙሉ ለዓለም አቀፉ የአቶሚክ ኢነርጂ ኤጀንሲ የደኅንነት ጥበቃ ሥርዓት ተገዢና ሰላማዊ መሆኑን በመጥቀስ፣ አሜሪካ ዓለም አቀፍ ሕግን በግልጽ መጣሷን አስታውቃለች።
በአሜሪካ የአየር ጥቃቶች ሳቢያ እስካሁን በኢራን ቢያንስ 50 ሰዎች መገደላቸውንና ከ500 በላይ መቁሰላቸውን የገለጸው የሀገሪቱ ጤና ሚኒስቴር፣ በርካታ ድልድዮችና ሲቪል መሠረተ-ልማቶች መውደማቸውን አረጋግጧል።
ለአሜሪካ ጥቃት የኢራን ወታደራዊ ምላሽ ፈጣንና መጠነ-ሰፊ የነበረ ሲሆን፣ የኢራን እስላማዊ አብዮታዊ ጥበቃ ኃይል "ናስር-2" የተሰኘውንና 20ኛ ምዕራፍ ላይ የደረሰውን የሚሳኤልና የድሮን ጥቃት የሰነዘረ ሲሆን፣ የኢራን መደበኛ ጦር በበኩሉ "ሳዕቃ" የተሰኘውን 15ኛ ምዕራፍ የጥቃት ዘመቻ አካሂዷል።
በጥቃቶቹ በኩዌት የሚገኘው አሊ አል-ሳሌም የአየር ኃይል ሰፈር፣ ካምፕ አሪፍጃን፣ ካምፕ አዳይሪ እና ሚና አብዱላህ የተሰኘው የሎጂስቲክስ ማዕከል በከባድ ሁኔታ ተመተዋል።
ከዚህም በተጨማሪ፣ በባህሬን የሚገኘው የአሜሪካ አምስተኛ ፍሊት ዋና መሥሪያ ቤት እና በዮርዳኖስ በሚገኘው አል-አዝራቅ የአየር ኃይል ሰፈር ላይ ጥቃት ተፈጽሟል። ምንም እንኳ የአሜሪካ እና የባሕረ-ሰላጤው አገራት መከላከያ ተቋማት አብዛኞቹን የኢራን ሚሳኤሎችና ድሮኖች ማክሸፋቸውን በይፋ ቢገልጹም፣ የወጡ የሳተላይት ምስሎች ግን የተለየ እውነታ እያሳዩ ነው።
የዋሽንግተን ፖስት የምርመራ ሪፖርት እንደሚያመለክተው፣ በክልሉ በሚገኙ 15 የአሜሪካ ወታደራዊ ይዞታዎች ውስጥ የራዳር ሥርዓቶች፣ የፓትሪዮት መከላከያ መሣሪያዎች እና የመጋዘን ተቋማትን ጨምሮ 228 መዋቅሮች በከፊልም ሆነ በሙሉ መውደማቸውን አረጋግጧል።
ይህ ወታደራዊ መካረር በዓለም አቀፍ ዲፕሎማሲና ኢኮኖሚ ላይ ከፍተኛ መናወጥን አስከትሏል። የኢራንን ይፋዊ አቤቱታ ተከትሎ፣ የዓለም አቀፉ አቶሚክ ኢነርጂ ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር ባወጡት መግለጫ፣ በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ጠቅላላ ጉባኤ ውሳኔዎች ቁጥር 444 እና 533 መሠረት፣ በሰላማዊ የኒውክሌር ተቋማት ላይ የሚሰነዘር ማንኛውም ጥቃት ዓለም አቀፍ ሕግን የሚጥስ መሆኑን አስታውሰዋል።
የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሐፊ በበኩላቸው፣ የኒውክሌር ተቋማትን ኢላማ ማድረግ የቀጣናውን ውጥረት ወደማይመለስ አደገኛ አደጋ ሊቀይረው እንደሚችል አስጠንቅቀው፣ የጸጥታው ምክር ቤት በአስቸኳይ እንዲመክርና ሁለቱም ወገኖች ራስን የመግታት እርምጃ እንዲወስዱ ጥሪ አቅርበዋል።
"የኒውክሌር መሠረተ-ልማቶችን ማጥቃት ቀጣናውን ብቻ ሳይሆን መላውን ዓለም ወደማይወጣበት ሁለንተናዊ ቀውስ ውስጥ የሚከት አደገኛ ድርጊት ነው" የሚለው የሰላም ጥሪ መግለጫ የሁኔታውን አሳሳቢነት በግልጽ ያሳያል።
በፖለቲካው ረገድ የሁለቱ ሀገራት መሪዎች የቃላት መለዋወጥ ይበልጥ ጠንክሯል። የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ዋሽንግተን በኩዌትና ባህሬን ላሉት የጦር ሰፈሮቿ ተጨማሪ የአየር መከላከያ ዘዴዎችን በፍጥነት ለማስፈር እያቀደች መሆኑን የገለጹ ሲሆን፣ ኢራን የኒውክሌር ታጣቂ እንድትሆን ፈጽሞ እንደማይፈቅዱ ተናግረዋል።
በሌላ በኩል፣ የኢራን መንፈሣዊ መሪ ሞጅታባ ኻሜኒ እና የፓርላማው አፈ-ጉባኤ መሀመድ ባቄር ቃሊባፍ፣ ዋሽንግተን ስምምነቱን በተጠቀሰው መሠረት ደጋግማ መጣሷ የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ፊርማ ፍጹም ዋጋ ቢስ መሆኑን ያረጋገጠ ነው ብለዋል። የሀገሪቱን ደኅንነት ለማረጋገጥ መላው የኢራን ሕዝብ ቅዱስ ያሉት "አንድነት" እንዲኖረው ጥሪ አቅርበዋል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ ዋሽንግተን በኢራን ወደቦች ላይ የባሕር እገዳ ለመጣል መሞከሯን ተከትሎ፣ ቴህራን በበኩሏ የዓለም የነዳጅ ንግድ ወሳኝ የደም ሥር የሆነውን የሆርሙዝ ሰርጥ ሙሉ በሙሉ ዝግ መሆኑን አውጃለች።
ይህንን የባሕረ-ሰላጤው መዘጋት ተከትሎ፣ የዓለም የነዳጅ ዋጋ (Brent Crude) በአንድ ጀምበር ከፍተኛ የዋጋ ጭማሪ አሳይቷል።
ዓለም አቀፍ የኢነርጂ ተንታኞች ውጥረቱ በዚህ የሚቀጥል ከሆነ በተለይ በእስያ እና በአውሮፓ አገራት ላይ ከባድ የነዳጅ እጥረትና የዋጋ ግሽበት ሊከሰት እንደሚችልና የንግድ መርከቦች ረጅም ርቀት ወደሚጠይቀው የአፍሪካ አቅጣጫ መስመራቸውን ለመቀየር እየተገደዱ መሆኑን እየገለጹ ይገኛሉ።
ፍጥጫው ወታደራዊ ጡንቻን ከማሳየት አልፎ የዓለምን መደበኛ የኢኮኖሚና የጸጥታ መዋቅር የቀየረ ታሪካዊ ቀውስ ሆኗል።
በሰለሞን ገዳ
19 days ago
ኢራን ከአሸማጋዮች የሰላም ዕቅድ እንደቀረበላት አስታወቀች
አሜሪካ እና ኢራንን በድጋሚ ወደ ተኩስ አቁም ስምምነት ለመመለስ ያቀዱት አሸማጋዮች፣ አዲስ የሰላም ዕቅድ ማቅረባቸውን ቴህራን አስታወቀች።
ሰኔ ላይ ጊዜያዊ የተኩስ አቁም ስምምነት ተፈራመው የነበሩት ሁለቱ አገራት፣ ላለፉት ሁለት ሳምንት ገደማ አንዳቸው በሌላቸው ላይ ከባድ ጥቃቶችን ሲፈጽሙ ቆይተዋል። የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕም ስምምነቱ አብቅቷል ብለዋል።
ይህንን ስምምነት ዳግም ለመመለስ ያቀዱት አሸማጋይ አገራት የ10 ቀናት የተኩስ አቁም እንዲደረግ የሚጠይቅ የሰላም ዕቅድ ማቅረባቸውን ዜና ወኪሉ ሮይተርስ ዘግቧል።
የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ኢስማኤል ባጋይ ዛሬ ሰኞ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ስለዚህ ጉዳይ ተጠይቀዋል። አሸማጋዮች ያዘጋጁትን ዕቅድ ለኢራን እንዳሳወቁ ቃል አቀባዩ አረጋግጠዋል።
“በአሸማጋዮች ስለዘተጋጁት ዕቅዶች ገለጻ ተደርጎል፤ ዕቅዱም ደርሶናል። ነገር ግን ለአሁኑ ወደ ዝርዝር ጉዳዮች ባንገባ ይሻላል” ሲሉ ተጨማሪ መረጃ ከመስጠት ተቆጥበዋል።
ባለፉት ቀናት ዲፕሎማሲያዊ እንቅስቃሴዎች እየተደረጉ መሆኑን የጠቆሙት ቃል አቀባዩ፤ “በአንዳንድ አሸማጋዮች የቀረቡ ዕቅዶች ለኢራን እስላማዊ ሪፐብሊክ መድረሳቸው የተረጋገጠ ነው” ብለዋል።
ፕሬዝዳንት ትራምፕ ወደፊት ለመደራደር የሚጠይቁ ከሆነ የኢራን ምላሽ ምን እንደሚሆንም ጥያቄ የቀረበላቸው ቃል አቀባዩ ኢስማኤል ባጋይ፣ “ዲፕሎማሲ ወይም ጦርነት” የሚል አማራጭ ለኢራን “ጠቃሚ አይደለም” ሲሉ ተናግረዋል።
“ራስን መከላከል ከዲፕሎማሲ ጋር አይጣጣምም ብሎ ማሰብ ትክክለኛ አመክንዮ አይደለም። [የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ] ሰይድ አባስ አራግቺ የሚያከናውኑት ሥራ እና [የመከላከያ ሚኒስትሩ] ሰይድ መጂድ የሚፈጽሙት ተግባር ተመሳሳይ ግብ የሚያሳኩ ናቸው” ብለዋል።
ባለፈው ሳምንት በመካከለኛው ምሥራቅ ጉብኝት ላይ የነበሩት የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ፤ ከጉዟቸው ሲመለሱ ከጋዜጠኞች ጋር በነበራቸው ቆይታ ዋሽንግተን “አሁንም ከኢራን ጋር ለሚደረግ ዲፕሎማሲያዊ መፍትሄ በሯ ክፍት” መሆኑን ተናግረው ነበር።
“ሁሌም ለዲፕሎማሲ ክፍት የሆንን ይመስለኛል። [መፍትሔው ግን] እውነተኛ መሆን አለበት። ልንገዛበት ፈቃደኛ የምንሆነው መሆን አለበት” ብለዋል።
ኢራን ሰኔ ላይ ለተፈረመው የመግባቢያ ስምምነት እንዳልተገዛች በመጥቀስ የከሰሱት ሩቢዮ፤ ሆርሙዝ ክፍት መሆን እንደነበረበት እንዲሁም በወሽመጡ የሚጓዙ መርከቦች ከጥቃት እና ከክፍያ ነጻ መሆን እንደነበረባቸው ገልጸዋል።
አሜሪካ ለዲፕሎማሲ ክፍት ስለመሆኗ የተነሳላቸው የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ኢስማኤል ባጋይ፣ “አሜሪካ ዲፕሎማሲ የምትለው ማስገደድ፣ ማስፈራራት፣ ዛቻ እና ማዕቀብ ነው” በማለት ተችተዋል።
BBC
አሜሪካ እና ኢራንን በድጋሚ ወደ ተኩስ አቁም ስምምነት ለመመለስ ያቀዱት አሸማጋዮች፣ አዲስ የሰላም ዕቅድ ማቅረባቸውን ቴህራን አስታወቀች።
ሰኔ ላይ ጊዜያዊ የተኩስ አቁም ስምምነት ተፈራመው የነበሩት ሁለቱ አገራት፣ ላለፉት ሁለት ሳምንት ገደማ አንዳቸው በሌላቸው ላይ ከባድ ጥቃቶችን ሲፈጽሙ ቆይተዋል። የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕም ስምምነቱ አብቅቷል ብለዋል።
ይህንን ስምምነት ዳግም ለመመለስ ያቀዱት አሸማጋይ አገራት የ10 ቀናት የተኩስ አቁም እንዲደረግ የሚጠይቅ የሰላም ዕቅድ ማቅረባቸውን ዜና ወኪሉ ሮይተርስ ዘግቧል።
የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ኢስማኤል ባጋይ ዛሬ ሰኞ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ስለዚህ ጉዳይ ተጠይቀዋል። አሸማጋዮች ያዘጋጁትን ዕቅድ ለኢራን እንዳሳወቁ ቃል አቀባዩ አረጋግጠዋል።
“በአሸማጋዮች ስለዘተጋጁት ዕቅዶች ገለጻ ተደርጎል፤ ዕቅዱም ደርሶናል። ነገር ግን ለአሁኑ ወደ ዝርዝር ጉዳዮች ባንገባ ይሻላል” ሲሉ ተጨማሪ መረጃ ከመስጠት ተቆጥበዋል።
ባለፉት ቀናት ዲፕሎማሲያዊ እንቅስቃሴዎች እየተደረጉ መሆኑን የጠቆሙት ቃል አቀባዩ፤ “በአንዳንድ አሸማጋዮች የቀረቡ ዕቅዶች ለኢራን እስላማዊ ሪፐብሊክ መድረሳቸው የተረጋገጠ ነው” ብለዋል።
ፕሬዝዳንት ትራምፕ ወደፊት ለመደራደር የሚጠይቁ ከሆነ የኢራን ምላሽ ምን እንደሚሆንም ጥያቄ የቀረበላቸው ቃል አቀባዩ ኢስማኤል ባጋይ፣ “ዲፕሎማሲ ወይም ጦርነት” የሚል አማራጭ ለኢራን “ጠቃሚ አይደለም” ሲሉ ተናግረዋል።
“ራስን መከላከል ከዲፕሎማሲ ጋር አይጣጣምም ብሎ ማሰብ ትክክለኛ አመክንዮ አይደለም። [የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ] ሰይድ አባስ አራግቺ የሚያከናውኑት ሥራ እና [የመከላከያ ሚኒስትሩ] ሰይድ መጂድ የሚፈጽሙት ተግባር ተመሳሳይ ግብ የሚያሳኩ ናቸው” ብለዋል።
ባለፈው ሳምንት በመካከለኛው ምሥራቅ ጉብኝት ላይ የነበሩት የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ፤ ከጉዟቸው ሲመለሱ ከጋዜጠኞች ጋር በነበራቸው ቆይታ ዋሽንግተን “አሁንም ከኢራን ጋር ለሚደረግ ዲፕሎማሲያዊ መፍትሄ በሯ ክፍት” መሆኑን ተናግረው ነበር።
“ሁሌም ለዲፕሎማሲ ክፍት የሆንን ይመስለኛል። [መፍትሔው ግን] እውነተኛ መሆን አለበት። ልንገዛበት ፈቃደኛ የምንሆነው መሆን አለበት” ብለዋል።
ኢራን ሰኔ ላይ ለተፈረመው የመግባቢያ ስምምነት እንዳልተገዛች በመጥቀስ የከሰሱት ሩቢዮ፤ ሆርሙዝ ክፍት መሆን እንደነበረበት እንዲሁም በወሽመጡ የሚጓዙ መርከቦች ከጥቃት እና ከክፍያ ነጻ መሆን እንደነበረባቸው ገልጸዋል።
አሜሪካ ለዲፕሎማሲ ክፍት ስለመሆኗ የተነሳላቸው የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ኢስማኤል ባጋይ፣ “አሜሪካ ዲፕሎማሲ የምትለው ማስገደድ፣ ማስፈራራት፣ ዛቻ እና ማዕቀብ ነው” በማለት ተችተዋል።
BBC
21 days ago
ኩዌት የኢራንን ጥቃት ተከትሎ በርካታ የእሳት አደጋ ሠራተኞች መጎዳታቸውን አስታወቀች
የኩዌት እሳት አደጋ መከላከያ ቅዳሜ ዕለት የተፈጸመውን የኢራን ጥቃት ተከትሎ የተቀሰቀሰ እሳትን ለማጥፋት የተሰማሩ በርካታ ሠራተኞች ጉዳት እንደ ደረሰባቸው አስታወቀ።
"የመጀመሪያው ክስተት እሳቱን ለማጥፋት ሲጥሩ የነበሩ የእሳት አደጋ ተከላካዮች እና አንድ ሲቪል ሠራተኛ ላይ በርካታ ጉዳቶችን አድርሷል" ሲል ድርጅቱ በመንግሥት ለሚተዳደረው የዜና ወኪል ኩና ተናግሯል።
ጥቃቱ የተፈጸመበት አካባቢ የነበሩ ሰዎች አካባቢውን እንዲለቅቁ የተደረጉ ሲሆን፣ የቆሰሉት ሰዎች አስፈላጊውን እርዳታ እንዲያገኙ ወደ ሕክምና ተቋም ተወስደዋል ሲል ጨምሮ ገልጿል።
የኩዌት ኤሌክትሪክ፣ ውሃ እና ታዳሽ ኃይል ሚኒስቴር፣ በኃይል ማመንጫው እና በውሃ ማጣሪያው ላይ ኢራን የፈጸመችወን ጥቃት ተከትሎ እሳት መቀስቀሱን አስታውቆ ነበር።
አሜሪካ ለሰባት ተከታታይ ሌሊት ጥቃት የፈጸመች ሲሆን ኢራንም በምላሹ የዩኤስ ጦር ኃይል መቀመጫ የሆኑ የቀጣናው አገራት ላይ ጥቃት ሰንዝራለች።
በዋሺንግተን እና ቴህራን መካከል ዳግም ጦርነት ያገረሸው በፓኪስታን አደራዳሪነት የተፈረመው የሰላም ስምምነት ውድቅ ከሆነ በኋላ ነው።
BBC
የኩዌት እሳት አደጋ መከላከያ ቅዳሜ ዕለት የተፈጸመውን የኢራን ጥቃት ተከትሎ የተቀሰቀሰ እሳትን ለማጥፋት የተሰማሩ በርካታ ሠራተኞች ጉዳት እንደ ደረሰባቸው አስታወቀ።
"የመጀመሪያው ክስተት እሳቱን ለማጥፋት ሲጥሩ የነበሩ የእሳት አደጋ ተከላካዮች እና አንድ ሲቪል ሠራተኛ ላይ በርካታ ጉዳቶችን አድርሷል" ሲል ድርጅቱ በመንግሥት ለሚተዳደረው የዜና ወኪል ኩና ተናግሯል።
ጥቃቱ የተፈጸመበት አካባቢ የነበሩ ሰዎች አካባቢውን እንዲለቅቁ የተደረጉ ሲሆን፣ የቆሰሉት ሰዎች አስፈላጊውን እርዳታ እንዲያገኙ ወደ ሕክምና ተቋም ተወስደዋል ሲል ጨምሮ ገልጿል።
የኩዌት ኤሌክትሪክ፣ ውሃ እና ታዳሽ ኃይል ሚኒስቴር፣ በኃይል ማመንጫው እና በውሃ ማጣሪያው ላይ ኢራን የፈጸመችወን ጥቃት ተከትሎ እሳት መቀስቀሱን አስታውቆ ነበር።
አሜሪካ ለሰባት ተከታታይ ሌሊት ጥቃት የፈጸመች ሲሆን ኢራንም በምላሹ የዩኤስ ጦር ኃይል መቀመጫ የሆኑ የቀጣናው አገራት ላይ ጥቃት ሰንዝራለች።
በዋሺንግተን እና ቴህራን መካከል ዳግም ጦርነት ያገረሸው በፓኪስታን አደራዳሪነት የተፈረመው የሰላም ስምምነት ውድቅ ከሆነ በኋላ ነው።
BBC
21 days ago
በርካታ የአሜሪካ ወታደሮች ተጎዱ‼️
ኢራን ጆርዳን በሚገኘው የአሜሪካ የጦር ቤዝ ላይ በፈፀመችው የሚሳኤል ጥቃት በርካታ ወታደሮች መጎዳታቸውን የአሜሪካ ባለስልጣናት እንዳረጋገጡለት ነገር ግን ቁጥሮቹን ለመግለፅ ፈቃደኛ እንዳልሆኑ CBS ዘግቧል።
አሜሪካ እና ኢራን ከባድ የተኩስ ልውውጥ ውስጥ ሲሆኑ አሜሪካ የኢራንን መሰረተ ልማት እና ድልድዮችን እያጠቃች ትገኛለች።
የኢራን ዋና የኤሌክትሪክ መስመር ጉዳት ያስተናገደ ሲሆን የቴህራን ዜጎች ኤሌክትሪክ ቆጥበው እንዲጠቀሙ ኢራን ለዜጎቿ መልዕክት አስተላልፋለች።
ኢራን በባህሬን እና ኩዬት የሚሳኤል ጥቃቷን የቀጠለች ሲሆን ኩዬት ለኢራን ጥቃት ምላሽ ለመስጠት ማቀዷን በመግለፅ ለዜጎቿ የጥንቃቄ መልዕክት አስተላልፋለች።
Seledadotio
Seledadotio
ኢራን ጆርዳን በሚገኘው የአሜሪካ የጦር ቤዝ ላይ በፈፀመችው የሚሳኤል ጥቃት በርካታ ወታደሮች መጎዳታቸውን የአሜሪካ ባለስልጣናት እንዳረጋገጡለት ነገር ግን ቁጥሮቹን ለመግለፅ ፈቃደኛ እንዳልሆኑ CBS ዘግቧል።
አሜሪካ እና ኢራን ከባድ የተኩስ ልውውጥ ውስጥ ሲሆኑ አሜሪካ የኢራንን መሰረተ ልማት እና ድልድዮችን እያጠቃች ትገኛለች።
የኢራን ዋና የኤሌክትሪክ መስመር ጉዳት ያስተናገደ ሲሆን የቴህራን ዜጎች ኤሌክትሪክ ቆጥበው እንዲጠቀሙ ኢራን ለዜጎቿ መልዕክት አስተላልፋለች።
ኢራን በባህሬን እና ኩዬት የሚሳኤል ጥቃቷን የቀጠለች ሲሆን ኩዬት ለኢራን ጥቃት ምላሽ ለመስጠት ማቀዷን በመግለፅ ለዜጎቿ የጥንቃቄ መልዕክት አስተላልፋለች።
Seledadotio
Seledadotio
Sponsored by
Surafel
22 days ago
የአሜሪካ ጥቃት ሰባት ሰዎችን መግደሉን ኢራን ገለጸች
አሜሪካ ለስድስተኛ ተከታታይ ምሽት በኢራን ላይ ጥቃት ማድረሷን ተከትሎ ቴህራን በርካታ ሰዎች መሞታቸውን የዘገበች ሲሆን፥ ጥቃቱ የሀገሪቱ ደቡባዊ ክፍል የመሠረተ ልማት አውታሮች ላይ ያነጣጠረ ነበር ተብሏል።
የአሜሪካ ማዕከላዊ እዝ ጥቃቱ «የኢራንን ወታደራዊ አቅም ለማዳከም» የተደረገ ጥረት ነዉ ብሏል፡፡
እነዚህ ጥቃቶች ሁለቱ ሀገራት ባለፈው ወር የተፈራረሙት ጊዜያዊ ስምምነት አደጋ ላይ መውደቁን ያሳያሉ።
የአሜሪካ ወታደራዊ ክፍል በኦማን ባሕረ ሰላጤ ላይ የእገዳ ጥሰት የሞከሩ ሶስት የንግድ መርከቦችን አቅጣጫ ማስቀየሩን እና አንዷን መርከብ ከጥቅም ውጭ ማድረጉን አስታውቋል።
በሌላ በኩል እንደ ኳታር፣ ዮርዳኖስ እና ባህሬን ያሉ የባሕረ ሰላጤው ሀገራት የመሠረተ ልማት ጥበቃቸውን እና ወታደራዊ ዝግጁነታቸውን እያጠናከሩ ነው።
የኢራን እስላማዊ አብዮታዊ ጥበቃ ጦር በአህቫዝ ከተማ ለሚገኝ የሕፃናት ካንሰር ሆስፒታል መፈናቀል ምላሽ ለመስጠት በባህሬን በሚገኝ የአሜሪካ አየር ኃይል ጣቢያ ላይ ጥቃት መፈጸሙን አስታውቋል።
የኢራን ጦር ቃል አቀባይ ብርጋዴር ጄኔራል መሐመድ አክራሚኒያ የአሜሪካ ጥቃቶች ከቀጠሉ የኢራን እርምጃ «ወደ አዳዲስ አካባቢዎች እንደሚስፋፋ» አስጠንቅቀዋል።
አሜሪካ ኢራን ወደ ድርድሩ እንድትመለስ ስትፈልግ፥ ኢራን ደግሞ አሜሪካ መጀመሪያ እገዳውን እንድታነሳ ትፈልጋለች።
የዋይት ሀውስ ፕሬስ ሴክሬተሪ ካሮሊን ሌቪት፤ ትራምፕ ኢራንን ተጠያቂ እንደሚያደርጉ ነገር ግን ሁልጊዜ ለዲፕሎማሲ ክፍት መሆናቸውን ገልጸው፥ መርከቦች ላይ የሚሰነዘር ጥቃትን ግን እንደማይፈቅዱ ተናግረዋል።
የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ግን በአሁኑ ወቅት ከዋሽንግተን ጋር ለመነጋገር ምንም ዓይነት እቅድ እንደሌለውና ትኩረቱ ሀገሪቱን መከላከል ላይ ብቻ መሆኑን አስታውቋል።
ሳራ ዮሐንስ
አሜሪካ ለስድስተኛ ተከታታይ ምሽት በኢራን ላይ ጥቃት ማድረሷን ተከትሎ ቴህራን በርካታ ሰዎች መሞታቸውን የዘገበች ሲሆን፥ ጥቃቱ የሀገሪቱ ደቡባዊ ክፍል የመሠረተ ልማት አውታሮች ላይ ያነጣጠረ ነበር ተብሏል።
የአሜሪካ ማዕከላዊ እዝ ጥቃቱ «የኢራንን ወታደራዊ አቅም ለማዳከም» የተደረገ ጥረት ነዉ ብሏል፡፡
እነዚህ ጥቃቶች ሁለቱ ሀገራት ባለፈው ወር የተፈራረሙት ጊዜያዊ ስምምነት አደጋ ላይ መውደቁን ያሳያሉ።
የአሜሪካ ወታደራዊ ክፍል በኦማን ባሕረ ሰላጤ ላይ የእገዳ ጥሰት የሞከሩ ሶስት የንግድ መርከቦችን አቅጣጫ ማስቀየሩን እና አንዷን መርከብ ከጥቅም ውጭ ማድረጉን አስታውቋል።
በሌላ በኩል እንደ ኳታር፣ ዮርዳኖስ እና ባህሬን ያሉ የባሕረ ሰላጤው ሀገራት የመሠረተ ልማት ጥበቃቸውን እና ወታደራዊ ዝግጁነታቸውን እያጠናከሩ ነው።
የኢራን እስላማዊ አብዮታዊ ጥበቃ ጦር በአህቫዝ ከተማ ለሚገኝ የሕፃናት ካንሰር ሆስፒታል መፈናቀል ምላሽ ለመስጠት በባህሬን በሚገኝ የአሜሪካ አየር ኃይል ጣቢያ ላይ ጥቃት መፈጸሙን አስታውቋል።
የኢራን ጦር ቃል አቀባይ ብርጋዴር ጄኔራል መሐመድ አክራሚኒያ የአሜሪካ ጥቃቶች ከቀጠሉ የኢራን እርምጃ «ወደ አዳዲስ አካባቢዎች እንደሚስፋፋ» አስጠንቅቀዋል።
አሜሪካ ኢራን ወደ ድርድሩ እንድትመለስ ስትፈልግ፥ ኢራን ደግሞ አሜሪካ መጀመሪያ እገዳውን እንድታነሳ ትፈልጋለች።
የዋይት ሀውስ ፕሬስ ሴክሬተሪ ካሮሊን ሌቪት፤ ትራምፕ ኢራንን ተጠያቂ እንደሚያደርጉ ነገር ግን ሁልጊዜ ለዲፕሎማሲ ክፍት መሆናቸውን ገልጸው፥ መርከቦች ላይ የሚሰነዘር ጥቃትን ግን እንደማይፈቅዱ ተናግረዋል።
የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ግን በአሁኑ ወቅት ከዋሽንግተን ጋር ለመነጋገር ምንም ዓይነት እቅድ እንደሌለውና ትኩረቱ ሀገሪቱን መከላከል ላይ ብቻ መሆኑን አስታውቋል።
ሳራ ዮሐንስ
23 days ago
ኢራን የሆርሙዝ ባህረ-ሰላጤን በቋሚነት እንደምትቆጣጠር አስታወቀች
የኢራን ባለስልጣናት በአሜሪካ እና በእስራኤል የተጀመረው ጦርነት ከመነሻው አንስቶ የሆርሙዝ ባህረ-ሰላጤን "ቀይ መስመር" ወይም ሊጣስ የማይገባ ወሳኝ ጉዳይ አድርገው ሲገልጹት ቆይተዋል። ብሪጋዲየር ጄኔራል ኢብራሂም ዞልፋጋሪ በሰጡት መግለጫም ይህንኑ አቋም የሚያጠናክር ነው።
የአሜሪካ ፕሬዝዳንት የኢራንን የኃይል ማመንጫና ማከፋፈያ መሰረተ-ልማቶች ስለማጥቃት በተደጋጋሚ መናገራቸው፣ ይህ መግለጫ የተሰጠዉ በወሳኝ ጊዜ እንዲሆን አድርጎታል።የወታደራዊው ዋና መስሪያ ቤት እንደገለጸው፣ አሜሪካ በኢራን መሰረተ-ልማቶች ላይ ተጨማሪ ጥቃቶችን ብትፈጽም፣ ኢራንም በአካባቢው የሚገኙ መሰረተ-ልማቶች ላይ የአጸፋ ጥቃት ትሰነዝራለች። ኢራን እስካሁን ይህን ያላደረገችው አቅም ስለሌላት ሳይሆን፣ የመታቀብ ፖሊሲ ስላላት ነው ፤ ነገር ግን አሜሪካ እንደዚህ አይነት ጥቃቶችን ከፈጸመች ያ የመታቀብ ፖሊሲ ያበቃል ሲል መስሪያ ቤቱ አክሏል።
የኢራን ዋና ተደራዳሪ እና የፓርላማ አፈ-ጉባኤ መሐመድ ባጌር ጋሊባፍ እንደተናገሩት፣ የኢራን ብሔራዊ ደህንነት በሆርሙዝ ባህረ-ሰላጤ ውስጥ "የኢራን አሰራሮችን" በመጠበቅ ላይ የተመሰረተ ሲሆን፣ "ጠላት" ይህንን በኃይል ለማዳከም እየሞከረ ነው ሲሉ ተደምጠዋል።ኢራናውያን የሚያወሩት ስለ ሆርሙዝ ጊዜያዊ ቁጥጥር አይደለም፤ ይልቁንም ለዓለም የሚያስተላልፉት መልእክት ኢራን በዚህ ስትራቴጂካዊ የውሃ መስመር ላይ ዘላቂ ቁጥጥር እና ሉዓላዊነት እንዲኖራት ነው። ይህ ደግሞ በቴህራን እና በዋሽንግተን መካከል ላለው ውጥረት ዋና ምክንያት ነው።
Seledadotio
Seledadotio
የኢራን ባለስልጣናት በአሜሪካ እና በእስራኤል የተጀመረው ጦርነት ከመነሻው አንስቶ የሆርሙዝ ባህረ-ሰላጤን "ቀይ መስመር" ወይም ሊጣስ የማይገባ ወሳኝ ጉዳይ አድርገው ሲገልጹት ቆይተዋል። ብሪጋዲየር ጄኔራል ኢብራሂም ዞልፋጋሪ በሰጡት መግለጫም ይህንኑ አቋም የሚያጠናክር ነው።
የአሜሪካ ፕሬዝዳንት የኢራንን የኃይል ማመንጫና ማከፋፈያ መሰረተ-ልማቶች ስለማጥቃት በተደጋጋሚ መናገራቸው፣ ይህ መግለጫ የተሰጠዉ በወሳኝ ጊዜ እንዲሆን አድርጎታል።የወታደራዊው ዋና መስሪያ ቤት እንደገለጸው፣ አሜሪካ በኢራን መሰረተ-ልማቶች ላይ ተጨማሪ ጥቃቶችን ብትፈጽም፣ ኢራንም በአካባቢው የሚገኙ መሰረተ-ልማቶች ላይ የአጸፋ ጥቃት ትሰነዝራለች። ኢራን እስካሁን ይህን ያላደረገችው አቅም ስለሌላት ሳይሆን፣ የመታቀብ ፖሊሲ ስላላት ነው ፤ ነገር ግን አሜሪካ እንደዚህ አይነት ጥቃቶችን ከፈጸመች ያ የመታቀብ ፖሊሲ ያበቃል ሲል መስሪያ ቤቱ አክሏል።
የኢራን ዋና ተደራዳሪ እና የፓርላማ አፈ-ጉባኤ መሐመድ ባጌር ጋሊባፍ እንደተናገሩት፣ የኢራን ብሔራዊ ደህንነት በሆርሙዝ ባህረ-ሰላጤ ውስጥ "የኢራን አሰራሮችን" በመጠበቅ ላይ የተመሰረተ ሲሆን፣ "ጠላት" ይህንን በኃይል ለማዳከም እየሞከረ ነው ሲሉ ተደምጠዋል።ኢራናውያን የሚያወሩት ስለ ሆርሙዝ ጊዜያዊ ቁጥጥር አይደለም፤ ይልቁንም ለዓለም የሚያስተላልፉት መልእክት ኢራን በዚህ ስትራቴጂካዊ የውሃ መስመር ላይ ዘላቂ ቁጥጥር እና ሉዓላዊነት እንዲኖራት ነው። ይህ ደግሞ በቴህራን እና በዋሽንግተን መካከል ላለው ውጥረት ዋና ምክንያት ነው።
Seledadotio
Seledadotio
23 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) አሜሪካ በኢራን የኃይልና የኤሌክትሪክ መሠረተ ልማቶች ላይ ወታደራዊ ጥቃት የምትሰነዝር ከሆነ፣ የየመኑ የሁቲ ታጣቂዎች በቀይ ባሕር በኩል የሚያልፈውን ዓለም አቀፍ የነዳጅ ማስተላለፊያ መስመር ለመዝጋት ተዋግተው እንዲጠብቁ ቴህራን ጥያቄ ማቅረቧን ሮይተርስ የዜና ወኪል ሦስት የውስጥ ምንጮችን ዋቢ አድርጎ ዘገበ። ይህ እርምጃ ቀደም ሲል ከተቀሰቀሰው ቀውስ ጋር ተዳምሮ በዓለም አቀፍ የነዳጅና የኃይል አቅርቦት ደኅንነት ላይ አዲስና እጅግ ከፍተኛ ስጋት ደቅኗል።
ይህ የውሳኔ ሐሳብ በኢስላማዊቷ ሪፐብሊክ (ኢራን) ከፍተኛ አመራሮች ዘንድ በስፋት ውይይት የተደረገበት ሲሆን፣ መልእክቱም ለሁቲ ታጣቂዎች መተላለፉን ሁለት ከፍተኛ የኢራን ባለሥልጣናትና ጉዳዩን በቅርብ የሚያውቁ የቀጠናው ምንጮች በምስጢር ገልጸዋል። ይሁን እንጂ ይህ ስልታዊ ጥያቄ ለሁቲዎች እንዴት እንደተላለፈና የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ባለፈው ማክሰኞ በኢራን መሠረተ ልማቶች ላይ ጥቃት ለመሰንዘር ካስጠነቀቁ በኋላ ስለመሆኑ በዝርዝር የተጠቀሰ ነገር የለም።
ለሁቲ ቡድን ቅርብ የሆኑ ምንጮች እንደገለጹት፣ ታጣቂዎቹ በቀይ ባሕር መግቢያ በሆነው በባቢል መንደብ ስትሬት አቅራቢያ፣ በሁደይዳ ከፍተኛ ቦታዎችና በዓደን ባሕረ ሰላጤ በሚያዋስኑ የመን ከፍተኛ ቦታዎች ላይ በርካታ ሚሳኤሎችንና ድሮኖችን (ሰው አልባ አውሮፕላኖችን) በማሰማራት በንግድ መርከቦች ላይ ጥቃት ለመሰንዘር ዝግጅታቸውን ሙሉ በሙሉ አጠናቀው ትዕዛዝ በመጠበቅ ላይ ናቸው። በየመን የሚገኙት የኢራን አብዮታዊ ጠባቂ ጦር (IRGC) ተወካዮች የባቢል መንደብ ስትሬት የሚዘጋበትን ትክክለኛ ጊዜ የመወሰን ሙሉ ሥልጣን እንደሚኖራቸውም ምንጩ አክሏል።
በአሁኑ ወቅት የሆርሙዝ ስትሬት በኢራን ሙሉ በሙሉ ተዘግቶ ባለበት ሁኔታ፣ ሁቲዎች በቀይ ባሕር የንግድ መርከቦች ወይም ወደቦች ላይ አዲስ ጥቃት የሚሰነዝሩ ከሆነ፣ የመካከለኛው ምስራቅ ሁለቱ ዋና ዋና የነዳጅ ኤክስፖርት መስመሮች በአንድ ጊዜ እንዲስተጓጎሉ ያደርጋል። ይህ ደግሞ በዓለም አቀፉ የኃይል ቀውስ ላይ እንዲሁም በኢራንና በአሜሪካ መካከል ባለው ሰፊ ግጭት ላይ አዲስና አስፈሪ ግንባር የሚከፍት ይሆናል።
የቀጠናው የፖለቲካ ተንታኞች እንደሚሉት፣ ቀይ ባሕርን መዝጋት ለሁቲዎች ከባድ አይሆንም። የተራቀቁ ሚሳኤሎች ባይኖሩ እንኳ ማንኛውም መሣሪያ የያዘ አካል በቀላሉ በባሕር ትራንስፖርት ፍሰቱ ላይ መስተጓጎል መፍጠር ይችላል።
ሳዑዲ ዓረቢያ የሆርሙዝ ስትሬት መዘጋቱን ተከትሎ፣ የነዳጅ አቅርቦቷ እንዳይቋረጥ 70 በመቶ የሚሆነውን የነዳጅ ኤክስፖርቷን በሀገር ውስጥ የፓይፕላይን መስመር ወደ ቀይ ባሕሩ የያንቡ ወደብ አዙራው ትገኛለች። በአሁኑ ወቅት ቀይ ባሕር 7 በመቶ የሚሆነውን የዓለም የኃይል አቅርቦት የሚሸከም በመሆኑ፣ በዚህ መስመር ላይ የሚሰነዘር ማንኛውም ጥቃት በዓለም የነዳጅ ገበያ ላይ ታይቶ የማይታወቅ የዋጋ ንረትና ቀውስ ያስከትላል። ሪላድ ይሄንን ከኢራንና ከሁቲዎች የሚሰነዘረውን ስጋት በጥብቅና በከፍተኛ ጥንቃቄ እየተከታተለችው መሆኑ ተነግሯል።
በቀጠናው ያለውን ውጥረት ይበልጥ ያባባሰው፣ ሁቲዎች ሳዑዲ ዓረቢያ በእነሱ ቁጥጥር ሥር የሚገኘውን አየር ማረፊያ በቦምብ ደብድባለች በሚል በመክሰስ፣ ባለፉት አራት ዓመታት የነበረውን የተኩስ አቁም ስምምነት በመጣስ ባለፈው ሰኞ ወደ ሳዑዲ ግዛት ሚሳኤሎችን መተኮሳቸው ነው። ይህ አጠቃላይ ቀውስ የጀመረው ባለፈው የካቲት 28 ቀን እስራኤልና አሜሪካ በኢራን ላይ ጥቃት ከሰነዘሩ በኋላ ቴህራን የዓለምን አንድ አምስተኛ የኃይል አቅርቦት የሚያስተላልፈውን የሆርሙዝ ስትሬት መዝጋቷን ተከትሎ እንደነበር ይታወሳል። በሰኔ ወር በቴህራንና በዋሽንግተን መካከል ተደርሶ የነበረው ደካማ የተኩስ አቁም ስምምነት መፍረሱን ተከትሎ ቀውሱ ወደ ሙሉ ጦርነት የማደግ ስጋቱ እጅግ አይሏል።
ይህ የውሳኔ ሐሳብ በኢስላማዊቷ ሪፐብሊክ (ኢራን) ከፍተኛ አመራሮች ዘንድ በስፋት ውይይት የተደረገበት ሲሆን፣ መልእክቱም ለሁቲ ታጣቂዎች መተላለፉን ሁለት ከፍተኛ የኢራን ባለሥልጣናትና ጉዳዩን በቅርብ የሚያውቁ የቀጠናው ምንጮች በምስጢር ገልጸዋል። ይሁን እንጂ ይህ ስልታዊ ጥያቄ ለሁቲዎች እንዴት እንደተላለፈና የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ባለፈው ማክሰኞ በኢራን መሠረተ ልማቶች ላይ ጥቃት ለመሰንዘር ካስጠነቀቁ በኋላ ስለመሆኑ በዝርዝር የተጠቀሰ ነገር የለም።
ለሁቲ ቡድን ቅርብ የሆኑ ምንጮች እንደገለጹት፣ ታጣቂዎቹ በቀይ ባሕር መግቢያ በሆነው በባቢል መንደብ ስትሬት አቅራቢያ፣ በሁደይዳ ከፍተኛ ቦታዎችና በዓደን ባሕረ ሰላጤ በሚያዋስኑ የመን ከፍተኛ ቦታዎች ላይ በርካታ ሚሳኤሎችንና ድሮኖችን (ሰው አልባ አውሮፕላኖችን) በማሰማራት በንግድ መርከቦች ላይ ጥቃት ለመሰንዘር ዝግጅታቸውን ሙሉ በሙሉ አጠናቀው ትዕዛዝ በመጠበቅ ላይ ናቸው። በየመን የሚገኙት የኢራን አብዮታዊ ጠባቂ ጦር (IRGC) ተወካዮች የባቢል መንደብ ስትሬት የሚዘጋበትን ትክክለኛ ጊዜ የመወሰን ሙሉ ሥልጣን እንደሚኖራቸውም ምንጩ አክሏል።
በአሁኑ ወቅት የሆርሙዝ ስትሬት በኢራን ሙሉ በሙሉ ተዘግቶ ባለበት ሁኔታ፣ ሁቲዎች በቀይ ባሕር የንግድ መርከቦች ወይም ወደቦች ላይ አዲስ ጥቃት የሚሰነዝሩ ከሆነ፣ የመካከለኛው ምስራቅ ሁለቱ ዋና ዋና የነዳጅ ኤክስፖርት መስመሮች በአንድ ጊዜ እንዲስተጓጎሉ ያደርጋል። ይህ ደግሞ በዓለም አቀፉ የኃይል ቀውስ ላይ እንዲሁም በኢራንና በአሜሪካ መካከል ባለው ሰፊ ግጭት ላይ አዲስና አስፈሪ ግንባር የሚከፍት ይሆናል።
የቀጠናው የፖለቲካ ተንታኞች እንደሚሉት፣ ቀይ ባሕርን መዝጋት ለሁቲዎች ከባድ አይሆንም። የተራቀቁ ሚሳኤሎች ባይኖሩ እንኳ ማንኛውም መሣሪያ የያዘ አካል በቀላሉ በባሕር ትራንስፖርት ፍሰቱ ላይ መስተጓጎል መፍጠር ይችላል።
ሳዑዲ ዓረቢያ የሆርሙዝ ስትሬት መዘጋቱን ተከትሎ፣ የነዳጅ አቅርቦቷ እንዳይቋረጥ 70 በመቶ የሚሆነውን የነዳጅ ኤክስፖርቷን በሀገር ውስጥ የፓይፕላይን መስመር ወደ ቀይ ባሕሩ የያንቡ ወደብ አዙራው ትገኛለች። በአሁኑ ወቅት ቀይ ባሕር 7 በመቶ የሚሆነውን የዓለም የኃይል አቅርቦት የሚሸከም በመሆኑ፣ በዚህ መስመር ላይ የሚሰነዘር ማንኛውም ጥቃት በዓለም የነዳጅ ገበያ ላይ ታይቶ የማይታወቅ የዋጋ ንረትና ቀውስ ያስከትላል። ሪላድ ይሄንን ከኢራንና ከሁቲዎች የሚሰነዘረውን ስጋት በጥብቅና በከፍተኛ ጥንቃቄ እየተከታተለችው መሆኑ ተነግሯል።
በቀጠናው ያለውን ውጥረት ይበልጥ ያባባሰው፣ ሁቲዎች ሳዑዲ ዓረቢያ በእነሱ ቁጥጥር ሥር የሚገኘውን አየር ማረፊያ በቦምብ ደብድባለች በሚል በመክሰስ፣ ባለፉት አራት ዓመታት የነበረውን የተኩስ አቁም ስምምነት በመጣስ ባለፈው ሰኞ ወደ ሳዑዲ ግዛት ሚሳኤሎችን መተኮሳቸው ነው። ይህ አጠቃላይ ቀውስ የጀመረው ባለፈው የካቲት 28 ቀን እስራኤልና አሜሪካ በኢራን ላይ ጥቃት ከሰነዘሩ በኋላ ቴህራን የዓለምን አንድ አምስተኛ የኃይል አቅርቦት የሚያስተላልፈውን የሆርሙዝ ስትሬት መዝጋቷን ተከትሎ እንደነበር ይታወሳል። በሰኔ ወር በቴህራንና በዋሽንግተን መካከል ተደርሶ የነበረው ደካማ የተኩስ አቁም ስምምነት መፍረሱን ተከትሎ ቀውሱ ወደ ሙሉ ጦርነት የማደግ ስጋቱ እጅግ አይሏል።
24 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ኢራን ወደ ድርድር የማትመጣ ከሆነ በመጪው ሳምንት በሀገሪቱ የኃይል ማመንጫዎች እና ድልድዮች ላይ ከባድ ጥቃት እንደሚፈጽሙ አስጠንቅቀዋል። ፕሬዝዳንቱ ይህንን የተናገሩት ሁለቱ ሀገራት ለተከታታይ አራት ቀናት ወታደራዊ ጥቃቶችን በተለዋወጡበት ወቅት ሲሆን፤ ኢራን ወደ ጠረጴዛው መጥታ ካልተደራደረች በስተቀር ምንም ነገር እንደማይተርፍላት ዝተዋል።
ከዚህ ቀደም በሆርሙዝ ሰርጥ በሚያልፉ መርከቦች ላይ የ20 በመቶ የመተላለፊያ ክፍያ ሊጥሉ እንደነበር የገለጹት ትራምፕ፣ ይህን ሀሳብ በመቀየር የባህረ ሰላጤው ሀገራት በአሜሪካ በሚያደርጉት ግዙፍ የንግድ እና ኢንቨስትመንት ስምምነት መተካቱን አስታውቀዋል። ይህንንም ተከትሎ አሜሪካ በኢራን ወደቦች ላይ የነበራትን የባህር ላይ እገዳ ዳግም መጀመሯን እና የአሜሪካ ማዕከላዊ እዝ በኢራን ላይ ተጨማሪ የአየር ጥቃቶችን መፈጸሙን አረጋግጧል።
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብዓዊ መብቶች ኃላፊ ቮልከር ቱርክ የትራምፕን ዛቻ ተከትለው በሰጡት ምላሽ፣ በዓለም አቀፍ ህግ መሰረት በሲቪል መሰረተ ልማቶች ላይ ሆን ተብሎ የሚፈጸም ጥቃት የጦር ወንጀል መሆኑን በማስታወስ ድርጊቱን ተችተዋል። በሌላ በኩል የኢራን ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ካዜም ጋሪባባዲ፣ አሜሪካ ወታደራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ጫናዋን በማጠናከር ኢራንን ወደ ድርድር እመልሳለሁ ብላ ማሰቧ ስህተት መሆኑን ገልጸዋል።
በቀጠናው ያለው ወታደራዊ ግጭት የንግድ መስመሩን ክፉኛ ያወከው ሲሆን፣ የኢራን እስላማዊ አብዮታዊ ዘብ በተባበሩት አረብ ኤሚሬቶች ሁለት ነዳጅ ጫኝ መርከቦች ላይ ባደረሰው የሚሳኤል ጥቃት አንድ የህንድ ዜግነት ያለው ሰራተኛ ሲገደል ስምንት ሰዎች ቆስለዋል። የኩዌት ጦር የኢራንን አጥቂ ድሮኖች ማክሸፉን ሲያሳውቅ፣ ባህሬንም የአየር ጥቃት ማስጠንቀቂያ ሳይረን አሰምታለች። ቴህራን በበኩሏ በባህሬን እና ዮርዳኖስ በሚገኙ የአሜሪካ የጦር ሰፈሮች ላይ ጥቃት ማድረሷን አስታውቃለች። ይህ ተከታታይ ግጭት በዓለም አቀፍ የንግድ መስመር በሆነው የሆርሙዝ ሰርጥ የመርከቦች እንቅስቃሴን ወደ ሁለት ወር ዝቅተኛ ደረጃ ያወረደው ሲሆን፣ የነዳጅ ዋጋም በከፍተኛ ሁኔታ እንዲያሻቅብ አድርጎታል።
ከዚህ ቀደም በሆርሙዝ ሰርጥ በሚያልፉ መርከቦች ላይ የ20 በመቶ የመተላለፊያ ክፍያ ሊጥሉ እንደነበር የገለጹት ትራምፕ፣ ይህን ሀሳብ በመቀየር የባህረ ሰላጤው ሀገራት በአሜሪካ በሚያደርጉት ግዙፍ የንግድ እና ኢንቨስትመንት ስምምነት መተካቱን አስታውቀዋል። ይህንንም ተከትሎ አሜሪካ በኢራን ወደቦች ላይ የነበራትን የባህር ላይ እገዳ ዳግም መጀመሯን እና የአሜሪካ ማዕከላዊ እዝ በኢራን ላይ ተጨማሪ የአየር ጥቃቶችን መፈጸሙን አረጋግጧል።
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብዓዊ መብቶች ኃላፊ ቮልከር ቱርክ የትራምፕን ዛቻ ተከትለው በሰጡት ምላሽ፣ በዓለም አቀፍ ህግ መሰረት በሲቪል መሰረተ ልማቶች ላይ ሆን ተብሎ የሚፈጸም ጥቃት የጦር ወንጀል መሆኑን በማስታወስ ድርጊቱን ተችተዋል። በሌላ በኩል የኢራን ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ካዜም ጋሪባባዲ፣ አሜሪካ ወታደራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ጫናዋን በማጠናከር ኢራንን ወደ ድርድር እመልሳለሁ ብላ ማሰቧ ስህተት መሆኑን ገልጸዋል።
በቀጠናው ያለው ወታደራዊ ግጭት የንግድ መስመሩን ክፉኛ ያወከው ሲሆን፣ የኢራን እስላማዊ አብዮታዊ ዘብ በተባበሩት አረብ ኤሚሬቶች ሁለት ነዳጅ ጫኝ መርከቦች ላይ ባደረሰው የሚሳኤል ጥቃት አንድ የህንድ ዜግነት ያለው ሰራተኛ ሲገደል ስምንት ሰዎች ቆስለዋል። የኩዌት ጦር የኢራንን አጥቂ ድሮኖች ማክሸፉን ሲያሳውቅ፣ ባህሬንም የአየር ጥቃት ማስጠንቀቂያ ሳይረን አሰምታለች። ቴህራን በበኩሏ በባህሬን እና ዮርዳኖስ በሚገኙ የአሜሪካ የጦር ሰፈሮች ላይ ጥቃት ማድረሷን አስታውቃለች። ይህ ተከታታይ ግጭት በዓለም አቀፍ የንግድ መስመር በሆነው የሆርሙዝ ሰርጥ የመርከቦች እንቅስቃሴን ወደ ሁለት ወር ዝቅተኛ ደረጃ ያወረደው ሲሆን፣ የነዳጅ ዋጋም በከፍተኛ ሁኔታ እንዲያሻቅብ አድርጎታል።
25 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) በመካከለኛው ምስራቅ ኢንስቲትዩት ከፍተኛ ተመራማሪ የሆኑት አሌክስ ቫታንካ እንዳስረዱት በአሜሪካ እና በኢራን መካከል ሰኔ 16 የተደረሰው የተኩስ አቁም ስምምነት ከመጀመሪያውም በቀላሉ ሊፈርስ የሚችል ነበር። ተመራማሪው ለአልጀዚራ በሰጡት ቃል ሁለቱ ወገኖች ጡንቻቸውን ማሳየት በሚፈልጉበት ጊዜ ሁሉ ግጭቶቹ የሚከሰቱት በሆርሙዝ ሰርጥ አካባቢ መሆኑን ጠቅሰው፣ ይህም በአሁኑ ወቅት የኢራን "ዋነኛ የመጫወቻ ካርድ" መሆኑን አስረድተዋል።
የአሜሪካን አቋም በተመለከተ ፕሬዝዳንት ትራምፕ "ኢራናውያን በቂ ቅጣት ካገኙ ሀሳባቸውን ቀይረው ወደ ድርድር ይመለሳሉ" በሚል ቁማር እየተጫወቱ መሆኑን ቫታንካ ተናግረዋል። ሆኖም ኢራን ለሚደርስባት ጫና እጅ ከመስጠት ይልቅ ሁሌም አጸፋዊ እርምጃ እንደምትወስድ በማሳየቷ፣ ይህ የአሜሪካ አካሄድ ወደ ከፋ ግጭት ሊያመራ እንደሚችል አስጠንቅቀዋል።
በሆርሙዝ ሰርጥ ዙሪያ ያለው አለመግባባት የሉዓላዊነት ጥያቄ ተደርጎ መወሰዱን አስመልክቶ ተመራማሪው ሲያብራሩ፣ ሰርጡ በአሜሪካ እና በእስራኤል ጥቃቶች ከመፈጸማቸው በፊት የሉዓላዊነት ጥያቄ እንዳልነበር እና ኢራን ከጥቃቱ በኋላ የተረፋት ብቸኛ አማራጭ በመሆኑ ብቻ ወደ ሉዓላዊነት ጉዳይነት እንደተቀየረ አብራርተዋል። የኢራን የኒውክሌር ፕሮግራም ከወደመ በኋላ ቴህራን ከአሜሪካ ጋር ለመደራደር የተረፋት ትልቅ አቅም ይኸው የሆርሙዝ ሰርጥ መሆኑን የጠቀሱት ቫታንካ፣ በዚህም ሳቢያ ኢራን በሰርጡ ላይ በክልሉና በዓለም አቀፍ ደረጃ ትልቅ ተጽዕኖ ፈጣሪ የመሆን አቅም እንዳላት መገንዘቧን አመልክተዋል። በመጨረሻም የዲፕሎማሲው ሂደት የመሳካት እድል እስካለው ድረስ ኢራን ይህንን ቁልፍ የመጫወቻ ካርዷን መጠቀም እንደምትቀጥል ግምታቸውን አስቀምጠዋል።
የአሜሪካን አቋም በተመለከተ ፕሬዝዳንት ትራምፕ "ኢራናውያን በቂ ቅጣት ካገኙ ሀሳባቸውን ቀይረው ወደ ድርድር ይመለሳሉ" በሚል ቁማር እየተጫወቱ መሆኑን ቫታንካ ተናግረዋል። ሆኖም ኢራን ለሚደርስባት ጫና እጅ ከመስጠት ይልቅ ሁሌም አጸፋዊ እርምጃ እንደምትወስድ በማሳየቷ፣ ይህ የአሜሪካ አካሄድ ወደ ከፋ ግጭት ሊያመራ እንደሚችል አስጠንቅቀዋል።
በሆርሙዝ ሰርጥ ዙሪያ ያለው አለመግባባት የሉዓላዊነት ጥያቄ ተደርጎ መወሰዱን አስመልክቶ ተመራማሪው ሲያብራሩ፣ ሰርጡ በአሜሪካ እና በእስራኤል ጥቃቶች ከመፈጸማቸው በፊት የሉዓላዊነት ጥያቄ እንዳልነበር እና ኢራን ከጥቃቱ በኋላ የተረፋት ብቸኛ አማራጭ በመሆኑ ብቻ ወደ ሉዓላዊነት ጉዳይነት እንደተቀየረ አብራርተዋል። የኢራን የኒውክሌር ፕሮግራም ከወደመ በኋላ ቴህራን ከአሜሪካ ጋር ለመደራደር የተረፋት ትልቅ አቅም ይኸው የሆርሙዝ ሰርጥ መሆኑን የጠቀሱት ቫታንካ፣ በዚህም ሳቢያ ኢራን በሰርጡ ላይ በክልሉና በዓለም አቀፍ ደረጃ ትልቅ ተጽዕኖ ፈጣሪ የመሆን አቅም እንዳላት መገንዘቧን አመልክተዋል። በመጨረሻም የዲፕሎማሲው ሂደት የመሳካት እድል እስካለው ድረስ ኢራን ይህንን ቁልፍ የመጫወቻ ካርዷን መጠቀም እንደምትቀጥል ግምታቸውን አስቀምጠዋል።
Sponsored by
Surafel
26 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ አሜሪካ ዓለም አቀፍ የነዳጅ ንግድ የጀርባ አጥንት የሆነውን የሆርሙዝ ሰርጥ መቆጣጠር እንዳለባት አስታወቁ። ይህ የተሰማው አሜሪካ እና ኢራን በቁልፍ የውሃ መስመሩ ላይ እያደረጉት ያለው ወታደራዊ ፍጥጫ እጅግ እየተባባሰ በመጣበት ወቅት ነው።
ትራምፕ ዛሬ ሰኞ ከ'Fox & Friends' ጋር በስልክ ባደረጉት ቃለ ምልልስ፣ "ሰርጡን እንጠብቀዋለን፤ ምናልባትም እኛ እናስተዳድረዋለን። የሰርጡ 'ጠባቂ መልአክ' እንሆናለን" ብለዋል። አሜሪካ ይህንን ጥበቃ በማድረጓ ከሌሎች ሀገራት ወጪዋ ሊተካላት (ካሳ ሊከፈላት) እንደሚገባም አክለዋል።
ይህን ተከትሎም አሜሪካ በኢራን ላይ የባህር ላይ እገዳ ዳግም መጣሏን ያወጁት ፕሬዝዳንቱ፣ በሰርጡ ለሚያልፉ የጭነት መርከቦች ለደህንነት ጥበቃ ወጪ የሚውል የ20 በመቶ ታክስ እንደሚጣል አስታውቀዋል።
የሀገራቱ ፍጥጫ የነዳጅ ዋጋን ሰኞ ጠዋት ከ3 በመቶ በላይ አሻቅቦታል። ዓለም አቀፍ መለኪያ የሆነው የብሬንት ድፍድፍ ነዳጅ ዋጋ ባለፈው ሳምንት ከነበረበት 71.99 ዶላር በአንድ በርሜል ወደ 80 ዶላር ተጠግቷል። ምንም እንኳን ዋጋው በሚያዝያ ወር ጦርነቱ አይሎ በነበረበት ወቅት ከተመዘገበው የ126 ዶላር ከፍተኛ ጣሪያ አሁንም ዝቅተኛ ቢሆንም፣ በአካባቢው ያለው የጸጥታ ስጋት "እጅግ አደገኛ" ደረጃ ላይ መድረሱ በዓለም ገበያ ላይ ከፍተኛ መደናገጥ ፈጥሯል። በአውሮፓ፣ በእስያ እና በዎል ስትሪት የአክሲዮን ገበያዎችም ማሽቆልቆል ታይቷል።
የአሜሪካ ጦር ቅዳሜ ምሽት ባወጣው መግለጫ፣ የኢራን ኃይሎች በቆጵሮስ ባንዲራ በምትጓዝ የንግድ መርከብ ላይ ጥቃት መፈጸማቸውን ተከትሎ በኢራን ላይ "የዚህን ሳምንት ሶስተኛ ዙር ጥቃት" መሰንዘሩን አስታውቋል። እሁድ ከሰዓት በኋላ ደግሞ ቴህራን በኦማን የባህር ዳርቻ ሌላ መርከብ ከጥቅም ውጪ ማድረጓን ተከትሎ፣ የኢራንን የማጥቃት አቅም ለማዳከም አሜሪካ ተጨማሪ ጥቃቶችን አድርሳለች።
ኢራን በበኩሏ በባህሬን፣ ኩዌት፣ ዮርዳኖስ እና ኦማን በሚገኙ የአሜሪካ ተቋማት ላይ የአጸፋ ጥቃት አድርሳለች። የአሜሪካ ባህር ኃይል 5ኛ እዝ በሚገኝባት ባህሬን እና በዮርዳኖስ፣ ከኢራን የተተኮሱ በርካታ ሚሳኤሎችን በአየር ላይ ማክሸፍ መቻሉ ተዘግቧል።
የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ እስማኤል ባጋይ፣ ኢራን የሰላም ስምምነቱን በመጣስ የመጀመሪያዋ እንዳልሆነች ተከራክረዋል።
ቴህራን በሳምንቱ መጨረሻ የሆርሙዝ ሰርጥን መዝጋቷን ያሳወቀች ሲሆን፣ የኢራን አብዮታዊ ዘብ የውሃ መስመሩ ዳግም ሙሉ በሙሉ ሊከፈት የሚችለው "የአሜሪካ ጦር ጠብ አጫሪ ጣልቃ ገብነት ሲያበቃ ብቻ ነው" ብሏል። ትራምፕ በበኩላቸው ሰርጡ ክፍት ነው ብለው ቢከራከሩም፣ የንግድ መርከቦች እንቅስቃሴ ግን በእጅጉ ቀንሷል። 'Kpler' የተባለው የመርከቦች ክትትል መረጃ እንደሚያሳየው፣ ከጦርነቱ በፊት በቀን 138 መርከቦች ያልፉበት ከነበረው መስመር፣ እሁድ ዕለት ያለፉት 6 መርከቦች ብቻ ናቸው።
ባለፈው ሰኔ 17 አሜሪካ እና ኢራን ለ60 ቀናት የሚቆይ ጊዜያዊ የተኩስ አቁም ስምምነት (MoU) ተፈራርመው የነበረ ቢሆንም፣ ይህ ስምምነት አሁን ላይ ሙሉ በሙሉ የፈረሰ ይመስላል። የተኩስ አቁም ስምምነቱ እስከ ነሐሴ አጋማሽ ድረስ ለመቆየት ታስቦ የነበረ ቢሆንም፣ ትራምፕ ባለፈው ሳምንት በኔቶ ጉባኤ ላይ ስምምነቱ "አብቅቷል" ማለታቸውን ተከትሎ የሰላም ድርድሩ ተስፋ ጨልሟል።
ትራምፕ ዛሬ ሰኞ ከ'Fox & Friends' ጋር በስልክ ባደረጉት ቃለ ምልልስ፣ "ሰርጡን እንጠብቀዋለን፤ ምናልባትም እኛ እናስተዳድረዋለን። የሰርጡ 'ጠባቂ መልአክ' እንሆናለን" ብለዋል። አሜሪካ ይህንን ጥበቃ በማድረጓ ከሌሎች ሀገራት ወጪዋ ሊተካላት (ካሳ ሊከፈላት) እንደሚገባም አክለዋል።
ይህን ተከትሎም አሜሪካ በኢራን ላይ የባህር ላይ እገዳ ዳግም መጣሏን ያወጁት ፕሬዝዳንቱ፣ በሰርጡ ለሚያልፉ የጭነት መርከቦች ለደህንነት ጥበቃ ወጪ የሚውል የ20 በመቶ ታክስ እንደሚጣል አስታውቀዋል።
የሀገራቱ ፍጥጫ የነዳጅ ዋጋን ሰኞ ጠዋት ከ3 በመቶ በላይ አሻቅቦታል። ዓለም አቀፍ መለኪያ የሆነው የብሬንት ድፍድፍ ነዳጅ ዋጋ ባለፈው ሳምንት ከነበረበት 71.99 ዶላር በአንድ በርሜል ወደ 80 ዶላር ተጠግቷል። ምንም እንኳን ዋጋው በሚያዝያ ወር ጦርነቱ አይሎ በነበረበት ወቅት ከተመዘገበው የ126 ዶላር ከፍተኛ ጣሪያ አሁንም ዝቅተኛ ቢሆንም፣ በአካባቢው ያለው የጸጥታ ስጋት "እጅግ አደገኛ" ደረጃ ላይ መድረሱ በዓለም ገበያ ላይ ከፍተኛ መደናገጥ ፈጥሯል። በአውሮፓ፣ በእስያ እና በዎል ስትሪት የአክሲዮን ገበያዎችም ማሽቆልቆል ታይቷል።
የአሜሪካ ጦር ቅዳሜ ምሽት ባወጣው መግለጫ፣ የኢራን ኃይሎች በቆጵሮስ ባንዲራ በምትጓዝ የንግድ መርከብ ላይ ጥቃት መፈጸማቸውን ተከትሎ በኢራን ላይ "የዚህን ሳምንት ሶስተኛ ዙር ጥቃት" መሰንዘሩን አስታውቋል። እሁድ ከሰዓት በኋላ ደግሞ ቴህራን በኦማን የባህር ዳርቻ ሌላ መርከብ ከጥቅም ውጪ ማድረጓን ተከትሎ፣ የኢራንን የማጥቃት አቅም ለማዳከም አሜሪካ ተጨማሪ ጥቃቶችን አድርሳለች።
ኢራን በበኩሏ በባህሬን፣ ኩዌት፣ ዮርዳኖስ እና ኦማን በሚገኙ የአሜሪካ ተቋማት ላይ የአጸፋ ጥቃት አድርሳለች። የአሜሪካ ባህር ኃይል 5ኛ እዝ በሚገኝባት ባህሬን እና በዮርዳኖስ፣ ከኢራን የተተኮሱ በርካታ ሚሳኤሎችን በአየር ላይ ማክሸፍ መቻሉ ተዘግቧል።
የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ እስማኤል ባጋይ፣ ኢራን የሰላም ስምምነቱን በመጣስ የመጀመሪያዋ እንዳልሆነች ተከራክረዋል።
ቴህራን በሳምንቱ መጨረሻ የሆርሙዝ ሰርጥን መዝጋቷን ያሳወቀች ሲሆን፣ የኢራን አብዮታዊ ዘብ የውሃ መስመሩ ዳግም ሙሉ በሙሉ ሊከፈት የሚችለው "የአሜሪካ ጦር ጠብ አጫሪ ጣልቃ ገብነት ሲያበቃ ብቻ ነው" ብሏል። ትራምፕ በበኩላቸው ሰርጡ ክፍት ነው ብለው ቢከራከሩም፣ የንግድ መርከቦች እንቅስቃሴ ግን በእጅጉ ቀንሷል። 'Kpler' የተባለው የመርከቦች ክትትል መረጃ እንደሚያሳየው፣ ከጦርነቱ በፊት በቀን 138 መርከቦች ያልፉበት ከነበረው መስመር፣ እሁድ ዕለት ያለፉት 6 መርከቦች ብቻ ናቸው።
ባለፈው ሰኔ 17 አሜሪካ እና ኢራን ለ60 ቀናት የሚቆይ ጊዜያዊ የተኩስ አቁም ስምምነት (MoU) ተፈራርመው የነበረ ቢሆንም፣ ይህ ስምምነት አሁን ላይ ሙሉ በሙሉ የፈረሰ ይመስላል። የተኩስ አቁም ስምምነቱ እስከ ነሐሴ አጋማሽ ድረስ ለመቆየት ታስቦ የነበረ ቢሆንም፣ ትራምፕ ባለፈው ሳምንት በኔቶ ጉባኤ ላይ ስምምነቱ "አብቅቷል" ማለታቸውን ተከትሎ የሰላም ድርድሩ ተስፋ ጨልሟል።
26 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) ባለሀብቶች በመካከለኛው ምስራቅ እየተባባሰ ለመጣው ውጥረት ምላሽ መስጠታቸውን ተከትሎ፣ ዛሬ ሰኞ ጠዋት የአሜሪካ የአክሲዮን ገበያዎች ማሽቆልቆል አሳይተዋል። የዋጋ ግሽበት ስጋትን ተከትሎ ሦስቱም ዋና ዋና የአክሲዮን ገበያ ጠቋሚዎች (Dow Jones, Nasdaq, እና S&P 500) የቀነሱ ሲሆን፣ ዓለም አቀፍ መለኪያ የሆነው የብሬንት ድፍድፍ ነዳጅ ዋጋ ከ4 በመቶ በላይ ጭማሪ በማሳየት አንድ በርሜል 79 ዶላር አካባቢ ደርሷል።
አሜሪካ እና ኢራን በሳምንቱ መጨረሻ የጥቃት ልውውጦችን ዳግም የጀመሩ ሲሆን፣ ቴህራን ለዓለም አቀፍ ንግድ ቁልፍ መተላለፊያ የሆነውን የሆርሙዝ ሰርጥ መዝጋቷን አስታውቃለች። ይሁን እንጂ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ የውሃ መስመሩ ክፍት ሆኖ እንደሚቀጥል እና በኢራን ወደቦች ላይ እገዳ ዳግም እንደሚጥሉ ተናግረዋል። ይህ እገዳ የኢራን መርከቦች ወይም ደንበኞች ወደቦቹን እንዳይጠቀሙ የሚያግድ ቢሆንም፣ የ20 በመቶ የጭነት ታክስ ለሚከፍሉ የሌሎች ሀገራት መርከቦች ግን ክፍት እንደሚሆን ፕሬዝዳንቱ አብራርተዋል።
ጦርነቱ ከተቀሰቀሰበት ጊዜ አንስቶ በዓለም አቀፍ የነዳጅ አቅርቦት ላይ የተፈጠረው ስጋት የነዳጅ ዋጋ ከፍተኛ መዋዠቅ እንዲያሳይ አድርጎታል። ምንም እንኳን ዋጋው በቅርብ ጊዜ በተሰሙት ዜናዎች ምክንያት ጭማሪ ቢያሳይም፣ አሁንም ባለፈው ግንቦት ወር ከነበረበት ደረጃ በእጅጉ ያነሰ ነው።
በተጨማሪም የአሜሪካ የአክሲዮን ገበያዎች የቴክኖሎጂ እና የማይክሮቺፕ አምራች ኩባንያዎች ወሩን በከባድ ፈተና መጀመራቸው ተጽዕኖ አሳድሮባቸዋል። ባለሀብቶች በኩባንያዎቹ የተጋነነ የዋጋ ተመን እና በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ (AI) ቴክኖሎጂ ያልተጨበጠ የገበያ ግለት ዙሪያ እያመነቱ ይገኛሉ። በዚህም የተነሳ የNvidia ፣ ስፔስ ኤክስ እና ኢንቴል አክሲዮኖች በጠዋቱ የግብይት ክፍለ ጊዜ ቅናሽ አሳይተዋል።
አሜሪካ እና ኢራን በሳምንቱ መጨረሻ የጥቃት ልውውጦችን ዳግም የጀመሩ ሲሆን፣ ቴህራን ለዓለም አቀፍ ንግድ ቁልፍ መተላለፊያ የሆነውን የሆርሙዝ ሰርጥ መዝጋቷን አስታውቃለች። ይሁን እንጂ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ የውሃ መስመሩ ክፍት ሆኖ እንደሚቀጥል እና በኢራን ወደቦች ላይ እገዳ ዳግም እንደሚጥሉ ተናግረዋል። ይህ እገዳ የኢራን መርከቦች ወይም ደንበኞች ወደቦቹን እንዳይጠቀሙ የሚያግድ ቢሆንም፣ የ20 በመቶ የጭነት ታክስ ለሚከፍሉ የሌሎች ሀገራት መርከቦች ግን ክፍት እንደሚሆን ፕሬዝዳንቱ አብራርተዋል።
ጦርነቱ ከተቀሰቀሰበት ጊዜ አንስቶ በዓለም አቀፍ የነዳጅ አቅርቦት ላይ የተፈጠረው ስጋት የነዳጅ ዋጋ ከፍተኛ መዋዠቅ እንዲያሳይ አድርጎታል። ምንም እንኳን ዋጋው በቅርብ ጊዜ በተሰሙት ዜናዎች ምክንያት ጭማሪ ቢያሳይም፣ አሁንም ባለፈው ግንቦት ወር ከነበረበት ደረጃ በእጅጉ ያነሰ ነው።
በተጨማሪም የአሜሪካ የአክሲዮን ገበያዎች የቴክኖሎጂ እና የማይክሮቺፕ አምራች ኩባንያዎች ወሩን በከባድ ፈተና መጀመራቸው ተጽዕኖ አሳድሮባቸዋል። ባለሀብቶች በኩባንያዎቹ የተጋነነ የዋጋ ተመን እና በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ (AI) ቴክኖሎጂ ያልተጨበጠ የገበያ ግለት ዙሪያ እያመነቱ ይገኛሉ። በዚህም የተነሳ የNvidia ፣ ስፔስ ኤክስ እና ኢንቴል አክሲዮኖች በጠዋቱ የግብይት ክፍለ ጊዜ ቅናሽ አሳይተዋል።
26 days ago
ኢራን “በአሜሪካ ጫና” ምክንያት ሆርሙዝን በተመለከተ ከኦማን ጋር ስምምነት ላይ አለመድረሷን ገለጸች
ኢራን እና ኦማን በሆርሙዝ ወሽመጥ የሚደረግ የመርከቦች ጉዞን በተመለከተ ያደረጉት ንግግር ያደረጉት “በአሜሪካ ጫና” ምክንያት ስምምነት ላይ መድረስ እንዳልቻሉ ቴህራን አስታወቀች።
በኢራን እና አሜሪካ ጦርነት እንዲሁም ድርድር የክርክር ማዕከል የሆነው የሆርሙዝ ወሽመጥ ከዓለም ነዳጅ እና ጋዝ ምርት ውስጥ 20 በመቶ ገደማው ይተላለፍበት የነበረ የወሳኝ የባሕር መስመር ነው። ከጦርነቱ ወዲህ በወሽመጡ ላይ ያላትን ቁጥጥር ያጠናከረችው ኢራን፤ በሆርሙዝ ሌላኛው ጫፍ ከአሁን በኋላ ከምትገኘው ኦማን ጋር በመነጋገር እንደምታስተዳድረው ስትናገር ቆይታለች።
የኢራን እና ኦማን ባለሥልጣናት ትናንት ቅዳሜ ዕለት የባሕር መስመሩን ትራፊክ አስተዳደር በተመለከተ መወያየታቸው ተገልጾ ነበር።
የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቃል አቀባይ ኢስማኢል ባቃኢ ዛሬ ሰኞ ውይይቱን አስመልክቶ በሰጡት መግለጫ፤ በኦማን ዋና ከተማ በተካሄደው ውይይት ስምምነት ላይ አለመደረሱን አስታውቀዋል። ቃል አቀባዩ፤ “ቅዳሜ ዕለት ሙስካት ውስጥ የተደረገው ንግግር [ከአሜሪካ ጋር በተፈረመው] የመግባቢያ ስምምነት አንቀጽ 5 ላይ በሚገኘው የሆርሙዝ ወሽመጥ ጉዳይ ላይ ብቻ ያተኮረ ነበር” ብለዋል።
አክለውም፤ “አሜሪካ ግልጽ እና ድብቅ በኦማን ላይ ባሳደረችው ጫና ምክንያት መከናወን የነበረበት ነገር ባለመሳካቱ እና ባለመፈጸሙ እናዝናለን" ሲሉ ዋሽንግተንን ተጠያቂ አድርገዋል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ፤ ኢራን ሆርሙዝ በድጋሚ መዘጋቱን ካስታወቀች በኋላ ከትናንት ምሽት አንስቶ እስካሁን ምንም መርከብ በወሽመጡ እንዳላለፈ ‘ማሪን ትራፊክ’ ከተሰኘው የመርከቦች ጉዞ መከታተያ ድረ ገጽ የተገኘው መረጃ አሳይቷል።
ኢራን የአሜሪካ ጦር በሚያደርገው “ሕገ ወጥ እንቅስቃሴ” ምክንያት በአሁኑ ሰዓት በሆርሙዝ በኩል ጉዞ ማድረግ “የማይቻል” መሆኑን በትናንትናው ዕለት ገልጻ ነበር።
አሜሪካ በበኩሏ ወሳኙ የባሕር መተላለፊያ ክፍት ነው በሚል አቋሟ ጸንታለች። የአሜሪካ ማዕከላዊ እዛ በወጣው መግለጫ ሆርሙዝ ክፍት እንደሆነ እንዲሁም ጦሩ የመርከብ ጉዞ ነጻነትን ለማስጠበቅ ዝግጁ መሆኑን ገልጿል።
BBC
ኢራን እና ኦማን በሆርሙዝ ወሽመጥ የሚደረግ የመርከቦች ጉዞን በተመለከተ ያደረጉት ንግግር ያደረጉት “በአሜሪካ ጫና” ምክንያት ስምምነት ላይ መድረስ እንዳልቻሉ ቴህራን አስታወቀች።
በኢራን እና አሜሪካ ጦርነት እንዲሁም ድርድር የክርክር ማዕከል የሆነው የሆርሙዝ ወሽመጥ ከዓለም ነዳጅ እና ጋዝ ምርት ውስጥ 20 በመቶ ገደማው ይተላለፍበት የነበረ የወሳኝ የባሕር መስመር ነው። ከጦርነቱ ወዲህ በወሽመጡ ላይ ያላትን ቁጥጥር ያጠናከረችው ኢራን፤ በሆርሙዝ ሌላኛው ጫፍ ከአሁን በኋላ ከምትገኘው ኦማን ጋር በመነጋገር እንደምታስተዳድረው ስትናገር ቆይታለች።
የኢራን እና ኦማን ባለሥልጣናት ትናንት ቅዳሜ ዕለት የባሕር መስመሩን ትራፊክ አስተዳደር በተመለከተ መወያየታቸው ተገልጾ ነበር።
የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቃል አቀባይ ኢስማኢል ባቃኢ ዛሬ ሰኞ ውይይቱን አስመልክቶ በሰጡት መግለጫ፤ በኦማን ዋና ከተማ በተካሄደው ውይይት ስምምነት ላይ አለመደረሱን አስታውቀዋል። ቃል አቀባዩ፤ “ቅዳሜ ዕለት ሙስካት ውስጥ የተደረገው ንግግር [ከአሜሪካ ጋር በተፈረመው] የመግባቢያ ስምምነት አንቀጽ 5 ላይ በሚገኘው የሆርሙዝ ወሽመጥ ጉዳይ ላይ ብቻ ያተኮረ ነበር” ብለዋል።
አክለውም፤ “አሜሪካ ግልጽ እና ድብቅ በኦማን ላይ ባሳደረችው ጫና ምክንያት መከናወን የነበረበት ነገር ባለመሳካቱ እና ባለመፈጸሙ እናዝናለን" ሲሉ ዋሽንግተንን ተጠያቂ አድርገዋል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ፤ ኢራን ሆርሙዝ በድጋሚ መዘጋቱን ካስታወቀች በኋላ ከትናንት ምሽት አንስቶ እስካሁን ምንም መርከብ በወሽመጡ እንዳላለፈ ‘ማሪን ትራፊክ’ ከተሰኘው የመርከቦች ጉዞ መከታተያ ድረ ገጽ የተገኘው መረጃ አሳይቷል።
ኢራን የአሜሪካ ጦር በሚያደርገው “ሕገ ወጥ እንቅስቃሴ” ምክንያት በአሁኑ ሰዓት በሆርሙዝ በኩል ጉዞ ማድረግ “የማይቻል” መሆኑን በትናንትናው ዕለት ገልጻ ነበር።
አሜሪካ በበኩሏ ወሳኙ የባሕር መተላለፊያ ክፍት ነው በሚል አቋሟ ጸንታለች። የአሜሪካ ማዕከላዊ እዛ በወጣው መግለጫ ሆርሙዝ ክፍት እንደሆነ እንዲሁም ጦሩ የመርከብ ጉዞ ነጻነትን ለማስጠበቅ ዝግጁ መሆኑን ገልጿል።
BBC
26 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) በሆርሙዝ ሰርጥ ቁጥጥር ዙሪያ በአሜሪካ እና በኢራን መካከል በተቀሰቀሰው የቅርብ ጊዜ የጠብ ጭማሪ ሳቢያ የነዳጅ ዋጋ በከፍተኛ ሁኔታ ጨምሯል።
ዋሽንግተን እና ቴህራን በዚህ ወሳኝ የውሃ መስመር ላይ ባላቸው ፍጥጫ ሳቢያ ጥቃቶችን በተለዋወጡበት በሰኞው ዕለት፣ ዋናው ዓለም አቀፍ መለኪያ የሆነው የብሬንት ድፍድፍ ነዳጅ ዋጋ ከ4 በመቶ በላይ ጭማሪ አሳይቷል።
እስከ ግሪንዊች መደበኛ ሰዓት አቆጣጠር 03:00 ድረስ ለሴፕቴምበር ወር የሚቀርበው የብሬንት ነዳጅ ዋጋ በአንድ በርሜል $79.17 የደረሰ ሲሆን፣ ይህም ከሰኔ 22 ወዲህ የተመዘገበው ከፍተኛው የዋጋ መጠን መሆኑ ታውቋል።
ዋሽንግተን እና ቴህራን በዚህ ወሳኝ የውሃ መስመር ላይ ባላቸው ፍጥጫ ሳቢያ ጥቃቶችን በተለዋወጡበት በሰኞው ዕለት፣ ዋናው ዓለም አቀፍ መለኪያ የሆነው የብሬንት ድፍድፍ ነዳጅ ዋጋ ከ4 በመቶ በላይ ጭማሪ አሳይቷል።
እስከ ግሪንዊች መደበኛ ሰዓት አቆጣጠር 03:00 ድረስ ለሴፕቴምበር ወር የሚቀርበው የብሬንት ነዳጅ ዋጋ በአንድ በርሜል $79.17 የደረሰ ሲሆን፣ ይህም ከሰኔ 22 ወዲህ የተመዘገበው ከፍተኛው የዋጋ መጠን መሆኑ ታውቋል።
27 days ago
ዓለም በሆርሙዝ ማዕበል ስትናወጥ፤ ኢትዮጵያ በ‘ራስን የመቻል’ ስትራቴጂ የሰላም ተምሳሌት ሆና ብቅ ብላለች
*******************
የዓለም የኢኮኖሚ ደም ስር በሆነው የሆርሙዝ ሰርጥ ላይ የተደቀነው የጦርነት ደመና፣ በዓለም አቀፍ ደረጃ በነዳጅ አቅርቦትና በምግብ ዋጋ ላይ ከፍተኛ አደጋ እየፈጠረ ይገኛል።
የአሜሪካ እና የኢራን ወታደራዊ ፍጥጫ የዓለምን የባሕር መስመሮች ወደ ጦር አውድማነት ሲቀይራቸው፣ መላው ዓለም በከፍተኛ ሥጋት ውስጥ ተውጧል።
ይሁን እንጂ ይህ ዓለም አቀፍ ቀውስ ለኢትዮጵያ ሌላኛው የፈተና ምዕራፍ ሳይሆን፣ ዓመታትን ያስቆጠረውን ‘ራስን የመቻል’ አገራዊ ራዕይ በተግባር የምትፈትሽበትና የፅናቷን ጉልበት ለዓለም የምታሳይበት ወርቃማ ዕድል ሆኗል።
ባለፉት ወራት በአሜሪካ እና በኢራን መካከል የተፈጠረው የፖለቲካና የኢኮኖሚ ውጥረት ወደ ቀጥተኛ ወታደራዊ ግጭት ማምራቱ፣ የሆርሙዝ ሰርጥን እንደ ስትራቴጂካዊ መከላከያ መሣሪያ የተመለከተችው ኢራን ሰርጡን ለንግድ መርከቦች መዝጋቷን ተከትሎ፣ የዓለም የነዳጅ አቅርቦት 20 በመቶው አደጋ ውስጥ ወድቋል።
ይህ ሁኔታ በዓለም ላይ ያለው የኢነርጂ፣ የትራንስፖርትና የምግብ ዋጋ በከፍተኛ ሁኔታ እንዲንር በማድረግ፣ በርካታ ታዳጊ አገራትን ለከፍተኛ የኢኮኖሚ ጫና ዳርጓል።
ነገር ግን ኢትዮጵያ ይህንን ዓለም አቀፍ ቀውስ ከመጀመሪያውኑ አስቀድማ በመረዳት፣ በራሷ አቅም ላይ የተመሠረተ ጠንካራ የኢኮኖሚ ምሽግ በመገንባቷ፣ የማዕበሉ ተጽዕኖ በሀገራዊ ደኅንነቷ ላይ የሚያሳድረውን ጫና በከፍተኛ ደረጃ ለመቀነስ ችላለች።
ኢትዮጵያ በነዳጅ ላይ ያለውን ጥገኝነት ለመቀነስ የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብን የኤሌክትሪክ ኃይል አቅም በማጠናከርና የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎችን ወደ አገር ውስጥ በማስገባት የተከተለችው ስትራቴጂ፣ ዛሬ በሆርሙዝ ቀውስ ሳቢያ የዓለም የነዳጅ ዋጋ ሲናወጥ አገራዊ ዋስትና እየሆነላት ነው።
ከዚህም በላይ፣ የባሕር ትራንስፖርት መቆራረጥ የምግብ ዋስትናን አደጋ ላይ እንዳይጥል በማሰብ፣ በበጋ መስኖ የስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ታላቅ ስኬት፣ ኢትዮጵያን ከዓለም አቀፍ የምግብ አቅርቦት ሰንሰለት መቆራረጥ ነፃ አውጥቷታል።
በአሁኑ ወቅት በስንዴ ምርት ራስን መቻል ብቻ ሳይሆን፣ ወደ ውጭ ገበያ ምርቷን መላክ መጀመሯ፣ ታዳጊ አገራት በሕዝብ ጉልበትና በተፈጥሮ ሀብታቸው ተደራጅተው መቆም እንደሚችሉ የዓለምን ትኩረት የሳበ ትልቅ ማሳያ ነው።
በቴህራን ውስጣዊ መዋቅር ውስጥ እየታየ ያለው መከፋፈል እና የአሜሪካ ወታደራዊ የበላይነት በዲፕሎማሲያዊ መንገድ ሳይፈታ መቅረቱ፣ የሆርሙዝ ቀውስን ይበልጥ ውስብስብ አድርጎታል።
ይሁን እንጂ የዓለም የነዳጅና የምግብ ዋጋ ሲናወጥ፣ ኢትዮጵያ የምትከተለው የኢነርጂ፣ የምግብ ዋስትና እና ሚዛናዊ የዲፕሎማሲ ስልት፣ በዓለም አቀፍ ማዕበሎች ውስጥ እንዴት በፅናት መጓዝ እንደሚቻል መንገድ አመላካች ሆኗል።
የኢትዮጵያ ስትራቴጂካዊ ጽናት፣ የአንድ አገር ብልጽግና በውጫዊ ጫናዎች ላይ ሳይሆን፣ በውስጣዊ አቅም፣ በሕዝብ አንድነት እና በራዕይ መሪነት ላይ የተመሠረተ ሲሆን ብቻ ዘላቂ ሊሆን እንደሚችል ለዓለም ሕያው ምስክር ነው።
በሰለሞን ገዳ
*******************
የዓለም የኢኮኖሚ ደም ስር በሆነው የሆርሙዝ ሰርጥ ላይ የተደቀነው የጦርነት ደመና፣ በዓለም አቀፍ ደረጃ በነዳጅ አቅርቦትና በምግብ ዋጋ ላይ ከፍተኛ አደጋ እየፈጠረ ይገኛል።
የአሜሪካ እና የኢራን ወታደራዊ ፍጥጫ የዓለምን የባሕር መስመሮች ወደ ጦር አውድማነት ሲቀይራቸው፣ መላው ዓለም በከፍተኛ ሥጋት ውስጥ ተውጧል።
ይሁን እንጂ ይህ ዓለም አቀፍ ቀውስ ለኢትዮጵያ ሌላኛው የፈተና ምዕራፍ ሳይሆን፣ ዓመታትን ያስቆጠረውን ‘ራስን የመቻል’ አገራዊ ራዕይ በተግባር የምትፈትሽበትና የፅናቷን ጉልበት ለዓለም የምታሳይበት ወርቃማ ዕድል ሆኗል።
ባለፉት ወራት በአሜሪካ እና በኢራን መካከል የተፈጠረው የፖለቲካና የኢኮኖሚ ውጥረት ወደ ቀጥተኛ ወታደራዊ ግጭት ማምራቱ፣ የሆርሙዝ ሰርጥን እንደ ስትራቴጂካዊ መከላከያ መሣሪያ የተመለከተችው ኢራን ሰርጡን ለንግድ መርከቦች መዝጋቷን ተከትሎ፣ የዓለም የነዳጅ አቅርቦት 20 በመቶው አደጋ ውስጥ ወድቋል።
ይህ ሁኔታ በዓለም ላይ ያለው የኢነርጂ፣ የትራንስፖርትና የምግብ ዋጋ በከፍተኛ ሁኔታ እንዲንር በማድረግ፣ በርካታ ታዳጊ አገራትን ለከፍተኛ የኢኮኖሚ ጫና ዳርጓል።
ነገር ግን ኢትዮጵያ ይህንን ዓለም አቀፍ ቀውስ ከመጀመሪያውኑ አስቀድማ በመረዳት፣ በራሷ አቅም ላይ የተመሠረተ ጠንካራ የኢኮኖሚ ምሽግ በመገንባቷ፣ የማዕበሉ ተጽዕኖ በሀገራዊ ደኅንነቷ ላይ የሚያሳድረውን ጫና በከፍተኛ ደረጃ ለመቀነስ ችላለች።
ኢትዮጵያ በነዳጅ ላይ ያለውን ጥገኝነት ለመቀነስ የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብን የኤሌክትሪክ ኃይል አቅም በማጠናከርና የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎችን ወደ አገር ውስጥ በማስገባት የተከተለችው ስትራቴጂ፣ ዛሬ በሆርሙዝ ቀውስ ሳቢያ የዓለም የነዳጅ ዋጋ ሲናወጥ አገራዊ ዋስትና እየሆነላት ነው።
ከዚህም በላይ፣ የባሕር ትራንስፖርት መቆራረጥ የምግብ ዋስትናን አደጋ ላይ እንዳይጥል በማሰብ፣ በበጋ መስኖ የስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ታላቅ ስኬት፣ ኢትዮጵያን ከዓለም አቀፍ የምግብ አቅርቦት ሰንሰለት መቆራረጥ ነፃ አውጥቷታል።
በአሁኑ ወቅት በስንዴ ምርት ራስን መቻል ብቻ ሳይሆን፣ ወደ ውጭ ገበያ ምርቷን መላክ መጀመሯ፣ ታዳጊ አገራት በሕዝብ ጉልበትና በተፈጥሮ ሀብታቸው ተደራጅተው መቆም እንደሚችሉ የዓለምን ትኩረት የሳበ ትልቅ ማሳያ ነው።
በቴህራን ውስጣዊ መዋቅር ውስጥ እየታየ ያለው መከፋፈል እና የአሜሪካ ወታደራዊ የበላይነት በዲፕሎማሲያዊ መንገድ ሳይፈታ መቅረቱ፣ የሆርሙዝ ቀውስን ይበልጥ ውስብስብ አድርጎታል።
ይሁን እንጂ የዓለም የነዳጅና የምግብ ዋጋ ሲናወጥ፣ ኢትዮጵያ የምትከተለው የኢነርጂ፣ የምግብ ዋስትና እና ሚዛናዊ የዲፕሎማሲ ስልት፣ በዓለም አቀፍ ማዕበሎች ውስጥ እንዴት በፅናት መጓዝ እንደሚቻል መንገድ አመላካች ሆኗል።
የኢትዮጵያ ስትራቴጂካዊ ጽናት፣ የአንድ አገር ብልጽግና በውጫዊ ጫናዎች ላይ ሳይሆን፣ በውስጣዊ አቅም፣ በሕዝብ አንድነት እና በራዕይ መሪነት ላይ የተመሠረተ ሲሆን ብቻ ዘላቂ ሊሆን እንደሚችል ለዓለም ሕያው ምስክር ነው።
በሰለሞን ገዳ
27 days ago
ኢራን በድጋሚ ሆርሙዝ ወሽመጥን ስትዘጋ፤ አሜሪካ ቴህራን ላይ አዲስ ዙር ጥቃት ከፈተች
ኢራን በሆርሙዝ ወሽመጥ የሚያልፉ መርከቦችን መምታቷን ተከትሎ አሜሪካ ቴህራን ላይ አዲስ ዙር ጥቃት ከፈተች።
የኢራን እስላማዊ አብዮታዊ ዘብ፤ ቀጣይ መግለጫ እስከሚሰጥ ድረስ ወሳኙ የባሕር መተላለፊያ ሆርሙዝ ተዘግቶ እንደሚቆይ አስታውቋል።
ለአሜሪካ “ጥቃትም” ከባድ ምላሽ እንደሚሰጥ መግለጹን የኢራን የመንግሥት መገናኛ ብዙኃን ዘግበዋል።
አብዮታዊ ዘቡ፤ ዋሽንግተን ጥቃት በፈጸመች በሰዓታት ልዩነት በዮርዳኖስ የሚገኝ የአሜሪካ ጦር ሰፈር መምታቱን ገልጿል።
የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች፣ ኳታር፣ ኩዌት እና ባህሬን በበኩላቸው ከኢራን ለተተኮሱባቸው ሚሳዔሎች እና ድሮኖች ምላሽ እየሰጡ መሆኑን አስታውቀዋል።
ጋብ ብሎ የነበረው የሁለቱ አገራት ጦርነት በድጋሚ የተቀሰቀሰው በዚህ ሳምንት መጀመሪያ በሦስት ነዳጅ ጫኝ የንግድ መርከቦች ላይ ጥቃት ከደረሰ በኋላ ነው።
ለዚህ ጥቃት ምላሽ የሰጠችው አሜሪካ ኢራንን ከደበደበች በኋላ የጥቃት ልውውጡ አገርሽቷል።
የአሜሪካ ማዕከላዊ ዕዝ ባወጣው መግለጫ በዚህ ሳምንት ሦስተኛ ዙር ጥቃት የከፈተው የኢራን አብዮታዉ ዘብ የቆጵሮስ ሰንደቅ ዓላማን እያውለበለበ በሆርሙዝ ወሽመጥ ይጓዝ የነበረ መርከብን "በግልጽ ስላጠቃ" እንደሆነ ገልጿል።
'ኤምቪ ጂኤፍኤስ ጋላክሲ' የተባለው መርከብ የሞተር ክፍሉ ላይ በደረሰው ከፍተኛ ጉዳት የተነሳ “ጉዞውን መቀጠል እንዳልቻለ” ማዕከላዊ ዕዙ አስታውቋል። አንድ ሲቪል የመርከብ ሠራተኛ መጥፋቱንም ገልጿል።
እንደ ዕዙ ገለጻ ኢራን ላይ በተፈጸመው ጥቃት የሚሳዔል እና ድሮን ሠፈሮች፣ የኮሚዩኒኬሽን ኔትዎርኮች እንዲሁም የባሕር ኃይል የክትትል ሥፍራዎችን ጨምሮ 140 የቴህራን ወታደራዊ ዒላማዎች ተመትተዋል።
የኢራን አብዮታዊ ዘብ በበኩሉ የአሜሪካ ጥቃት "ደቡባዊ የባሕር ዳርቻ ላይ የሚገኙ በርካታ የባሕር ዳርቻ የጦር ሰፈሮችን እና የቴሌኮሚዩኒኬሽን ማማዎችን" ዒላማ ማድረጉን አስታውቋል።
ለዚህ ጥቃት በተሰጠው “የመጀመሪያ ዙር” ምላሽ፤ ዮርዳኖስ ውስጥ የሚገኘውን ‘ፕሪንስ ሀሰን’ የአየር ኃይል ጦር ሰፈር እንዲሁም ሌሎች ዒላማዎችን መምታቱን ገልጿል። እንደ ኢራን ገለጻ በጥቃቱ የጦር ሰፈሩ የዕዝ እና ቁጥጥር ማዕከል እንዲሁም የኤምኪው9 ድሮን ማቆሚያዎች ወድመዋል።
ከዚህ አስቀድሞ ኢራን የሆርሙዝ ወሽመጥን መዝጋቷን የአገሪቱ መንግሥት መገናኛ ብዙኃን ዘግበዋል።
ዘገባዎቹ እንደሚያስረዱት መተላለፊያው የተዘጋው የኢራን ጦር ባልተፈቀደ መስመር ለመጓዝ በሞከረ መርከብ ላይ ክሩዝ ሚሳዔል ካስወነጨፈ በኋላ ነው።
እንደ አብዮታዊ ዘቡ ገለጻ፤ መርከቡ የተሰጡትን ትዕዛዞች በተደጋጋሚ ችላ በማለቱ “በማስጠንቀቂያ ተኩስ እንዲመታ እና እንዲቆም” ተደርጓል።
ሆርሙዝ በመዘጋቱ ምክንያት ለሚፈጸም ማንኛው የአሜሪካ “ጥቃት”፤ የሚሰጠው ምላሽ “ከባድ” እንደሚሆን እና በቀጣናው የሚገኙ አዲስ የጦር ሰፈሮች ዒላማ እንደሚደረጉ አስጠንቅቆ ነበር።
BBC
ኢራን በሆርሙዝ ወሽመጥ የሚያልፉ መርከቦችን መምታቷን ተከትሎ አሜሪካ ቴህራን ላይ አዲስ ዙር ጥቃት ከፈተች።
የኢራን እስላማዊ አብዮታዊ ዘብ፤ ቀጣይ መግለጫ እስከሚሰጥ ድረስ ወሳኙ የባሕር መተላለፊያ ሆርሙዝ ተዘግቶ እንደሚቆይ አስታውቋል።
ለአሜሪካ “ጥቃትም” ከባድ ምላሽ እንደሚሰጥ መግለጹን የኢራን የመንግሥት መገናኛ ብዙኃን ዘግበዋል።
አብዮታዊ ዘቡ፤ ዋሽንግተን ጥቃት በፈጸመች በሰዓታት ልዩነት በዮርዳኖስ የሚገኝ የአሜሪካ ጦር ሰፈር መምታቱን ገልጿል።
የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች፣ ኳታር፣ ኩዌት እና ባህሬን በበኩላቸው ከኢራን ለተተኮሱባቸው ሚሳዔሎች እና ድሮኖች ምላሽ እየሰጡ መሆኑን አስታውቀዋል።
ጋብ ብሎ የነበረው የሁለቱ አገራት ጦርነት በድጋሚ የተቀሰቀሰው በዚህ ሳምንት መጀመሪያ በሦስት ነዳጅ ጫኝ የንግድ መርከቦች ላይ ጥቃት ከደረሰ በኋላ ነው።
ለዚህ ጥቃት ምላሽ የሰጠችው አሜሪካ ኢራንን ከደበደበች በኋላ የጥቃት ልውውጡ አገርሽቷል።
የአሜሪካ ማዕከላዊ ዕዝ ባወጣው መግለጫ በዚህ ሳምንት ሦስተኛ ዙር ጥቃት የከፈተው የኢራን አብዮታዉ ዘብ የቆጵሮስ ሰንደቅ ዓላማን እያውለበለበ በሆርሙዝ ወሽመጥ ይጓዝ የነበረ መርከብን "በግልጽ ስላጠቃ" እንደሆነ ገልጿል።
'ኤምቪ ጂኤፍኤስ ጋላክሲ' የተባለው መርከብ የሞተር ክፍሉ ላይ በደረሰው ከፍተኛ ጉዳት የተነሳ “ጉዞውን መቀጠል እንዳልቻለ” ማዕከላዊ ዕዙ አስታውቋል። አንድ ሲቪል የመርከብ ሠራተኛ መጥፋቱንም ገልጿል።
እንደ ዕዙ ገለጻ ኢራን ላይ በተፈጸመው ጥቃት የሚሳዔል እና ድሮን ሠፈሮች፣ የኮሚዩኒኬሽን ኔትዎርኮች እንዲሁም የባሕር ኃይል የክትትል ሥፍራዎችን ጨምሮ 140 የቴህራን ወታደራዊ ዒላማዎች ተመትተዋል።
የኢራን አብዮታዊ ዘብ በበኩሉ የአሜሪካ ጥቃት "ደቡባዊ የባሕር ዳርቻ ላይ የሚገኙ በርካታ የባሕር ዳርቻ የጦር ሰፈሮችን እና የቴሌኮሚዩኒኬሽን ማማዎችን" ዒላማ ማድረጉን አስታውቋል።
ለዚህ ጥቃት በተሰጠው “የመጀመሪያ ዙር” ምላሽ፤ ዮርዳኖስ ውስጥ የሚገኘውን ‘ፕሪንስ ሀሰን’ የአየር ኃይል ጦር ሰፈር እንዲሁም ሌሎች ዒላማዎችን መምታቱን ገልጿል። እንደ ኢራን ገለጻ በጥቃቱ የጦር ሰፈሩ የዕዝ እና ቁጥጥር ማዕከል እንዲሁም የኤምኪው9 ድሮን ማቆሚያዎች ወድመዋል።
ከዚህ አስቀድሞ ኢራን የሆርሙዝ ወሽመጥን መዝጋቷን የአገሪቱ መንግሥት መገናኛ ብዙኃን ዘግበዋል።
ዘገባዎቹ እንደሚያስረዱት መተላለፊያው የተዘጋው የኢራን ጦር ባልተፈቀደ መስመር ለመጓዝ በሞከረ መርከብ ላይ ክሩዝ ሚሳዔል ካስወነጨፈ በኋላ ነው።
እንደ አብዮታዊ ዘቡ ገለጻ፤ መርከቡ የተሰጡትን ትዕዛዞች በተደጋጋሚ ችላ በማለቱ “በማስጠንቀቂያ ተኩስ እንዲመታ እና እንዲቆም” ተደርጓል።
ሆርሙዝ በመዘጋቱ ምክንያት ለሚፈጸም ማንኛው የአሜሪካ “ጥቃት”፤ የሚሰጠው ምላሽ “ከባድ” እንደሚሆን እና በቀጣናው የሚገኙ አዲስ የጦር ሰፈሮች ዒላማ እንደሚደረጉ አስጠንቅቆ ነበር።
BBC
Comments