16 hours ago
ኢትዮጵያ እየተጠናቀቀ ባለው 2018 ዓ.ም ከ124 በላይ ዓለም አቀፍ ሜዳሊያዎች መገኘታቸውን ተገለጸ
#ethiopia | በኢትዮጵያ የስፖርት ዘርፍ አዲስ እይታን በመፍጠር፣ ህጋዊና መዋቅራዊ ማዕቀፎችን በማጠናከር እንዲሁም በርካታ ሀገር አቀፍና ዓለም አቀፍ ውድድሮችን በማስተናገድ የ2018 በጀት ዓመት አመርቂና ስኬታማ ጊዜ የነበረ መሆኑ ተገለጸ።
የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር የሚያካሄደው የባህል፣ ጥበባትና ስፖርት ጥናትና ምርምር ጉባኤ እንዲሁም ዓመታዊ የሴክተር ጉባኤ ላይ የባህል እና ስፖርት ሚኒስቴር የስፖርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ድኤታ አቶ መክዩ መሀመድ እንደገለጹት፣ የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ዓመታዊ የሴክተር ጉባኤ የታቀዱ ግቦችን በጋራ ለመገምገም እና ከክልል እስከ ፌደራል ያሉ ቅንጅታዊ አሰራሮችን ለማጠናከር ከፍተኛ አስተዋጽኦ አበርክቷል።
አክለውም ዘንድሮ የስፖርት ልማት ስራዎች በተሻለ መንገድ የተፈጸሙበትና በአጠቃላይ የስፖርት ዘመን ተብሎ ሊወሰድ የሚችልበት የስኬት ዓመት እንደነበር ጠቁመዋል።
የስፖርት ቤተሰቡ በተደጋጋሚ ያነሳቸው የነበሩ ህጋዊና አሰራር ነክ ጥያቄዎች ምላሽ ማግኘታቸውን የጠቆሙት ሚኒስትር ድኤታው፣ ሁሉንም ባለድርሻ አካላትና ምሁራንን ያሳተፈ አዲስ የስፖርት ፖሊሲ ተዘጋጅቶ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መጽደቁንና አዋጁም ወደ ትግበራ መግባቱን አስረድተዋል።
ይህ አዲስ ፖሊሲ የመንግስትን አመራር ሰጪነት፣ ከ139 ሺህ በላይ የሚሆኑ ህዝባዊ አደረጃጀቶችንና ማህበራትን አቅጣጫ፣ እንዲሁም የስፖርቱን እድገት የሚያፋጥነው የግል ባለሀብቶች ተሳትፎን በግልጽ የለየ አዲስ እይታ ይዞ መምጣቱንም አብራርተዋል።
ስፖርት ከሜዳ ውድድር ባለፈ የህዝቦች ወንድማማችነትን የሚገነባ፣ ሰላምና አንድነትን የሚያጠናክር ትልቅ የሀገር ልማት መሳሪያ መሆኑን የገለጹት አቶ መክዩ መሀመድ፣ በዚህ ዓመት በተካሄዱ 420 የክልል አቀፍ እና 118 ሀገር አቀፍ ውድድሮች ከአስር ሺዎች በላይ ስፖርተኞች መሳተፋቸውን ገልጸዋል። እነዚህ መድረኮች የወጡ አትሌቶችን ከማፍራት ባሻገር ሰላምን በመገንባትና ህዝቦችን በማቀራረብ ረገድ የጎላ ሚና እንደነበራቸው አብራርተዋል።
ህብረተሰቡን ንቁና ስፖርትን ባህል ያደረገ ለማድረግ በተሰራው ስራ የስፖርት አዘዋታሪው ህዝብ ቁጥር 24 በመቶ ወይም 32 ሚሊዮን ማድረስ መቻሉን ሚኒስትር ድኤታው ጠቁመዋል። ከዚህ በተጨማሪ ከኮሪደር ልማት ጋር በተያያዘ ከ45 ሺህ በላይ የስፖርት ፋሲሊቲዎች መገንባታቸውንና እነዚህንም በቴክኖሎጂ ዘመናዊ የማድረግ ስራ እየተከናወነ እንደሚገኝ ገልጸዋል።
በአለም አቀፍና ቀጠናዊ ውድድሮች የሀገሪቱን ስም የሚያስጠሩ አሸናፊ ብሄራዊ ቡድኖችን ለመገንባት በሚደረገው ጥረት አትሌቶቻችን ከ124 በላይ ሜዳሊያዎችን ማስመዝገባቸውን አቶ መክዩ መሀመድ አበክረው ገልጸዋል።
በተለይም በታዳጊዎች ልማት ላይ ትኩረት ተደርጎ እየተሰራ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት ከ45 ሺህ በላይ ታዳጊዎች በማሰልጠኛ ማዕከላት ውስጥ ስልጠና እየወሰዱ ይገኛሉ።
በተጨማሪም የስፖርት ቱሪዝምን ለማበራታት በተደረገው ጥረት ከ29 በላይ ዓለም አቀፍ ውድድሮችና ኮንፈረንሶች በኢትዮጵያ መካሄዳቸውንና ደረጃቸውን የጠበቁ ስታዲየሞች ግንባታም ትኩረት ተሰጥቶት እየተከናወነ መሆኑን ጠቅሰዋል።
ስፖርት ለሀገር ጂዲፒ እና ለስራ እድል ፈጠራ የሚያበረክተውን አስተዋጽኦ ለማሳደግ የተጀመሩ ጥናቶች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ አብራርተዋል።
በመጨረሻም፣ በአዲሱ ፖሊሲ የባህል ስፖርት ልዩ ትኩረት ማግኘቱንና በቀጣይ ዓመት ኢትዮጵያ የአፍሪካ የባህል ስፖርት ፌስቲቫልን በበላይነት እንደምታዘጋጅ አቶ መክዩ መሀመድ ገልጸው፤ ላመጣው ስኬት ለስፖርት ቤተሰቡና ለመገናኛ ብዙሃን አካላት ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
ጌትነት ተመስገን
📷 ከበደ መክብብ
#ethiopiansports #ethiopiasportpolicy #sportsdevelopment #ethiopia#youthinsports #sportinspiration
#ethiopia | በኢትዮጵያ የስፖርት ዘርፍ አዲስ እይታን በመፍጠር፣ ህጋዊና መዋቅራዊ ማዕቀፎችን በማጠናከር እንዲሁም በርካታ ሀገር አቀፍና ዓለም አቀፍ ውድድሮችን በማስተናገድ የ2018 በጀት ዓመት አመርቂና ስኬታማ ጊዜ የነበረ መሆኑ ተገለጸ።
የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር የሚያካሄደው የባህል፣ ጥበባትና ስፖርት ጥናትና ምርምር ጉባኤ እንዲሁም ዓመታዊ የሴክተር ጉባኤ ላይ የባህል እና ስፖርት ሚኒስቴር የስፖርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ድኤታ አቶ መክዩ መሀመድ እንደገለጹት፣ የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ዓመታዊ የሴክተር ጉባኤ የታቀዱ ግቦችን በጋራ ለመገምገም እና ከክልል እስከ ፌደራል ያሉ ቅንጅታዊ አሰራሮችን ለማጠናከር ከፍተኛ አስተዋጽኦ አበርክቷል።
አክለውም ዘንድሮ የስፖርት ልማት ስራዎች በተሻለ መንገድ የተፈጸሙበትና በአጠቃላይ የስፖርት ዘመን ተብሎ ሊወሰድ የሚችልበት የስኬት ዓመት እንደነበር ጠቁመዋል።
የስፖርት ቤተሰቡ በተደጋጋሚ ያነሳቸው የነበሩ ህጋዊና አሰራር ነክ ጥያቄዎች ምላሽ ማግኘታቸውን የጠቆሙት ሚኒስትር ድኤታው፣ ሁሉንም ባለድርሻ አካላትና ምሁራንን ያሳተፈ አዲስ የስፖርት ፖሊሲ ተዘጋጅቶ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መጽደቁንና አዋጁም ወደ ትግበራ መግባቱን አስረድተዋል።
ይህ አዲስ ፖሊሲ የመንግስትን አመራር ሰጪነት፣ ከ139 ሺህ በላይ የሚሆኑ ህዝባዊ አደረጃጀቶችንና ማህበራትን አቅጣጫ፣ እንዲሁም የስፖርቱን እድገት የሚያፋጥነው የግል ባለሀብቶች ተሳትፎን በግልጽ የለየ አዲስ እይታ ይዞ መምጣቱንም አብራርተዋል።
ስፖርት ከሜዳ ውድድር ባለፈ የህዝቦች ወንድማማችነትን የሚገነባ፣ ሰላምና አንድነትን የሚያጠናክር ትልቅ የሀገር ልማት መሳሪያ መሆኑን የገለጹት አቶ መክዩ መሀመድ፣ በዚህ ዓመት በተካሄዱ 420 የክልል አቀፍ እና 118 ሀገር አቀፍ ውድድሮች ከአስር ሺዎች በላይ ስፖርተኞች መሳተፋቸውን ገልጸዋል። እነዚህ መድረኮች የወጡ አትሌቶችን ከማፍራት ባሻገር ሰላምን በመገንባትና ህዝቦችን በማቀራረብ ረገድ የጎላ ሚና እንደነበራቸው አብራርተዋል።
ህብረተሰቡን ንቁና ስፖርትን ባህል ያደረገ ለማድረግ በተሰራው ስራ የስፖርት አዘዋታሪው ህዝብ ቁጥር 24 በመቶ ወይም 32 ሚሊዮን ማድረስ መቻሉን ሚኒስትር ድኤታው ጠቁመዋል። ከዚህ በተጨማሪ ከኮሪደር ልማት ጋር በተያያዘ ከ45 ሺህ በላይ የስፖርት ፋሲሊቲዎች መገንባታቸውንና እነዚህንም በቴክኖሎጂ ዘመናዊ የማድረግ ስራ እየተከናወነ እንደሚገኝ ገልጸዋል።
በአለም አቀፍና ቀጠናዊ ውድድሮች የሀገሪቱን ስም የሚያስጠሩ አሸናፊ ብሄራዊ ቡድኖችን ለመገንባት በሚደረገው ጥረት አትሌቶቻችን ከ124 በላይ ሜዳሊያዎችን ማስመዝገባቸውን አቶ መክዩ መሀመድ አበክረው ገልጸዋል።
በተለይም በታዳጊዎች ልማት ላይ ትኩረት ተደርጎ እየተሰራ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት ከ45 ሺህ በላይ ታዳጊዎች በማሰልጠኛ ማዕከላት ውስጥ ስልጠና እየወሰዱ ይገኛሉ።
በተጨማሪም የስፖርት ቱሪዝምን ለማበራታት በተደረገው ጥረት ከ29 በላይ ዓለም አቀፍ ውድድሮችና ኮንፈረንሶች በኢትዮጵያ መካሄዳቸውንና ደረጃቸውን የጠበቁ ስታዲየሞች ግንባታም ትኩረት ተሰጥቶት እየተከናወነ መሆኑን ጠቅሰዋል።
ስፖርት ለሀገር ጂዲፒ እና ለስራ እድል ፈጠራ የሚያበረክተውን አስተዋጽኦ ለማሳደግ የተጀመሩ ጥናቶች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ አብራርተዋል።
በመጨረሻም፣ በአዲሱ ፖሊሲ የባህል ስፖርት ልዩ ትኩረት ማግኘቱንና በቀጣይ ዓመት ኢትዮጵያ የአፍሪካ የባህል ስፖርት ፌስቲቫልን በበላይነት እንደምታዘጋጅ አቶ መክዩ መሀመድ ገልጸው፤ ላመጣው ስኬት ለስፖርት ቤተሰቡና ለመገናኛ ብዙሃን አካላት ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
ጌትነት ተመስገን
📷 ከበደ መክብብ
#ethiopiansports #ethiopiasportpolicy #sportsdevelopment #ethiopia#youthinsports #sportinspiration
2 days ago
በሳዑዲ ዓረቢያ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የነበሩ 1 ሺህ 672 ኢትዮጵያውያን ወደ ሀገራቸው ተመለሱ
በሳዑዲ ዓረቢያ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የነበሩ 1 ሺህ 672 ኢትዮያውያን በሳምንቱ ውስጥ በተደረገ 8 ዙር በረራ ወደ ሀገራቸው ተመልሰዋል።
ከተመላሾቹ መካከል 1 ሺህ 670 ወንዶች፣ 1 ሴት፣ 1 ጨቅላ ሕፃን እንዲሁም ዕድሜያቸው ከ18 ዓመት በታች የሆኑ 34 ታዳጊዎች ይገኙበታል።
መስከረም 5 ቀን 2018 ዓ.ም. በተጀመረው በዚህ ዜጎችን ወደ ሀገር ቤት የመመለስ ዘመቻ እስካሁን ከ90 ሺህ በላይ ኢትዮጵያውያንን መመለስ ተችሏል።
የሴቶችና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር እንዳስታወቀው፤ ሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውርን ለመከላከል፣ የኅብረተሰቡን ግንዛቤ ለማሳደግ እና ደኅንነቱ የተጠበቀ ፍልሰትን ለማበረታታት እየሠራ ይገኛል።
በተጨማሪም ከባለድርሻ አካላት ጋር በመቀናጀት ለተመላሾች በአየር ማረፊያና በማቆያ ማዕከላት አስፈላጊውን ድጋፍ በማድረግ ከቤተሰቦቻቸው ጋር የማቀላቀል ሥራው ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጿል።
Seledadotio
Seledadotio
በሳዑዲ ዓረቢያ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የነበሩ 1 ሺህ 672 ኢትዮያውያን በሳምንቱ ውስጥ በተደረገ 8 ዙር በረራ ወደ ሀገራቸው ተመልሰዋል።
ከተመላሾቹ መካከል 1 ሺህ 670 ወንዶች፣ 1 ሴት፣ 1 ጨቅላ ሕፃን እንዲሁም ዕድሜያቸው ከ18 ዓመት በታች የሆኑ 34 ታዳጊዎች ይገኙበታል።
መስከረም 5 ቀን 2018 ዓ.ም. በተጀመረው በዚህ ዜጎችን ወደ ሀገር ቤት የመመለስ ዘመቻ እስካሁን ከ90 ሺህ በላይ ኢትዮጵያውያንን መመለስ ተችሏል።
የሴቶችና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር እንዳስታወቀው፤ ሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውርን ለመከላከል፣ የኅብረተሰቡን ግንዛቤ ለማሳደግ እና ደኅንነቱ የተጠበቀ ፍልሰትን ለማበረታታት እየሠራ ይገኛል።
በተጨማሪም ከባለድርሻ አካላት ጋር በመቀናጀት ለተመላሾች በአየር ማረፊያና በማቆያ ማዕከላት አስፈላጊውን ድጋፍ በማድረግ ከቤተሰቦቻቸው ጋር የማቀላቀል ሥራው ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጿል።
Seledadotio
Seledadotio
2 days ago
(ዘ-ሐበሻ ስፖርት) የ'ሪያል ማድሪድ ፋውንዴሽን' በተጠናቀቀው የውድድር ዘመን በመላው አፍሪካ ካከናወናቸው ስኬታማ ተግባራት መካከል በኢትዮጵያ አዲስ የማህበራዊ ስፖርት አካዳሚ መክፈቱ በዋና ማሳያነት ተጠቅሷል። ፋውንዴሽኑ ኢትዮጵያን ጨምሮ በ23 የአፍሪካ ሀገራት ውስጥ 52 የማህበራዊ ስፖርት ፕሮጀክቶችን ያካሄደ ሲሆን፣ በዚህም 10,628 የሚሆኑ ህጻናትን፣ ታዳጊዎችን እና ወጣቶችን የዕድሉ ተጠቃሚ ማድረግ ችሏል።
በዘመኑ ከተመዘገቡት ትልልቅ ስኬቶች አንዱ በሀገራችን ኢትዮጵያ አዲስ የማህበራዊ ስፖርት አካዳሚ መከፈቱ ነው። ከኢትዮጵያ በተጨማሪም አንጎላ፣ ኬንያ፣ ዩጋንዳ፣ ታንዛኒያ፣ ሴኔጋል እና ግብጽን ጨምሮ በ23 የአፍሪካ ሀገራት ፕሮጀክቱ ተደራሽ ሆኗል።
በአካታችነት በኩል ፋውንዴሽኑ ሴት ታዳጊዎች በስፖርቱ ያላቸውን ተሳትፎ በማሳደግ እና ሴት አሰልጣኞችን በማበረታታት ላይ ልዩ ትኩረት ሰጥቷል። ከዚህም በተጨማሪ አካል ጉዳተኛ ህጻናት፣ ወጣት ስደተኞች እንዲሁም በከባድ ድህነት እና በግጭት የተጎዱ ማህበረሰቦችን የዕድሉ ተጠቃሚ አድርጓል። ከስፖርታዊ እንቅስቃሴዎች ባሻገር ትምህርታዊ ድጋፍን፣ ጤናማ የአኗኗር ዘይቤን፣ የህጻናት ጥበቃን፣ የጾታ እኩልነትን እና ማህበረሰባዊ ትስስርን ማጠናከር የትምህርት ቤቶቹ ዋነኛ የትኩረት አቅጣጫዎች ናቸው።
የአካባቢውን አሰልጣኞች አቅም በስልጠና፣ በክትትል እና በተሞክሮ ልውውጥ ማሳደግ የፕሮጀክቱ ሌላኛው ስኬት ነው። ይህ አካሄድ ከዚህ ቀደም የፕሮጀክቱ ተጠቃሚ የነበሩ ወጣቶች አሁን ላይ ለተተኪው ትውልድ አሰልጣኝ እና አርአያ የሚሆኑበትን ቀጣይነት ያለው ሞዴል ለመፍጠር አስችሏል።
ፋውንዴሽኑ ይህንን ዘላቂ እና አዎንታዊ ተጽዕኖ ለማምጣት ከተለያዩ ማህበራዊ ተቋማት፣ የኃይማኖት ተቋማት፣ ሌሎች ፋውንዴሽኖች፣ ኩባንያዎች እና የአካባቢው መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ጋር በቅንጅት ሲሰራ መቆየቱን አስታውቋል።
በዘመኑ ከተመዘገቡት ትልልቅ ስኬቶች አንዱ በሀገራችን ኢትዮጵያ አዲስ የማህበራዊ ስፖርት አካዳሚ መከፈቱ ነው። ከኢትዮጵያ በተጨማሪም አንጎላ፣ ኬንያ፣ ዩጋንዳ፣ ታንዛኒያ፣ ሴኔጋል እና ግብጽን ጨምሮ በ23 የአፍሪካ ሀገራት ፕሮጀክቱ ተደራሽ ሆኗል።
በአካታችነት በኩል ፋውንዴሽኑ ሴት ታዳጊዎች በስፖርቱ ያላቸውን ተሳትፎ በማሳደግ እና ሴት አሰልጣኞችን በማበረታታት ላይ ልዩ ትኩረት ሰጥቷል። ከዚህም በተጨማሪ አካል ጉዳተኛ ህጻናት፣ ወጣት ስደተኞች እንዲሁም በከባድ ድህነት እና በግጭት የተጎዱ ማህበረሰቦችን የዕድሉ ተጠቃሚ አድርጓል። ከስፖርታዊ እንቅስቃሴዎች ባሻገር ትምህርታዊ ድጋፍን፣ ጤናማ የአኗኗር ዘይቤን፣ የህጻናት ጥበቃን፣ የጾታ እኩልነትን እና ማህበረሰባዊ ትስስርን ማጠናከር የትምህርት ቤቶቹ ዋነኛ የትኩረት አቅጣጫዎች ናቸው።
የአካባቢውን አሰልጣኞች አቅም በስልጠና፣ በክትትል እና በተሞክሮ ልውውጥ ማሳደግ የፕሮጀክቱ ሌላኛው ስኬት ነው። ይህ አካሄድ ከዚህ ቀደም የፕሮጀክቱ ተጠቃሚ የነበሩ ወጣቶች አሁን ላይ ለተተኪው ትውልድ አሰልጣኝ እና አርአያ የሚሆኑበትን ቀጣይነት ያለው ሞዴል ለመፍጠር አስችሏል።
ፋውንዴሽኑ ይህንን ዘላቂ እና አዎንታዊ ተጽዕኖ ለማምጣት ከተለያዩ ማህበራዊ ተቋማት፣ የኃይማኖት ተቋማት፣ ሌሎች ፋውንዴሽኖች፣ ኩባንያዎች እና የአካባቢው መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ጋር በቅንጅት ሲሰራ መቆየቱን አስታውቋል።
3 days ago
በእንግሊዝኛ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ትምህርት የተማሩ ከ100 በላይ ታዳጊዎች ተመረቁ
#ethiopia | አዲስ አበባ – የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን መገናኛ ብዙኃን አገልግሎት ሥርጭት ድርጅት በቦሌ ኆኀተ ብርሃን ቅድስት ድንግል ማርያም ቤተክርስቲያን ላለፉት አምስት ሳምንታት በእንግሊዝኛ ቋንቋ መሠረታዊ የቤተክርስቲያን ትምህርት ሲከታተሉ የቆዩ ከ100 በላይ ታዳጊዎችን ሐምሌ 26 ቀን 2018 ዓ.ም. አስመርቋል።
በምረቃ ሥነ ሥርዓቱ ላይ የጉራጌ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ፣ የመገናኛ ብዙኃኑ ዋና ሥራ አስኪያጅ ዶ/ር ቀሲስ አካልወልድ ተሰማ እና የተመራቂዎቹ ቤተሰቦች ተገኝተዋል።
ተማሪዎቹ በእንግሊዝኛ ቋንቋ የቤተክርስቲያን ዶግማ፣ ቀኖና፣ ታሪክ እና የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት የተማሩ ሲሆን፣ መርሐ ግብሩ እምነቱን ለወጣቶች ዓለም አቀፍ ተደራሽነት ባለው መልኩ ለማስተላለፍ በማሰብ የተዘጋጀ መሆኑ ተገልጿል።
ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ በዚሁ ወቅት ባስተላለፉት አባታዊ መልዕክት፣ ታዳጊዎች የእምነታቸውን ትምህርት በእንግሊዝኛ መማራቸው ወደፊት በውጭ ሀገራት ቢኖሩም እምነታቸውን በቀላሉ እንዲረዱና እንዲያስተምሩ እንደሚያግዛቸው ገልጸዋል።
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን መገናኛ ብዙኃን አገልግሎት ሥርጭት ድርጅትም የወንጌል ትምህርቶችን በተለያዩ ቋንቋዎች ተደራሽ የማድረግ ሥራውን በቀጣይነት እንደሚያጠናክር አስታውቋል።
#ethiopia | አዲስ አበባ – የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን መገናኛ ብዙኃን አገልግሎት ሥርጭት ድርጅት በቦሌ ኆኀተ ብርሃን ቅድስት ድንግል ማርያም ቤተክርስቲያን ላለፉት አምስት ሳምንታት በእንግሊዝኛ ቋንቋ መሠረታዊ የቤተክርስቲያን ትምህርት ሲከታተሉ የቆዩ ከ100 በላይ ታዳጊዎችን ሐምሌ 26 ቀን 2018 ዓ.ም. አስመርቋል።
በምረቃ ሥነ ሥርዓቱ ላይ የጉራጌ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ፣ የመገናኛ ብዙኃኑ ዋና ሥራ አስኪያጅ ዶ/ር ቀሲስ አካልወልድ ተሰማ እና የተመራቂዎቹ ቤተሰቦች ተገኝተዋል።
ተማሪዎቹ በእንግሊዝኛ ቋንቋ የቤተክርስቲያን ዶግማ፣ ቀኖና፣ ታሪክ እና የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት የተማሩ ሲሆን፣ መርሐ ግብሩ እምነቱን ለወጣቶች ዓለም አቀፍ ተደራሽነት ባለው መልኩ ለማስተላለፍ በማሰብ የተዘጋጀ መሆኑ ተገልጿል።
ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ በዚሁ ወቅት ባስተላለፉት አባታዊ መልዕክት፣ ታዳጊዎች የእምነታቸውን ትምህርት በእንግሊዝኛ መማራቸው ወደፊት በውጭ ሀገራት ቢኖሩም እምነታቸውን በቀላሉ እንዲረዱና እንዲያስተምሩ እንደሚያግዛቸው ገልጸዋል።
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን መገናኛ ብዙኃን አገልግሎት ሥርጭት ድርጅትም የወንጌል ትምህርቶችን በተለያዩ ቋንቋዎች ተደራሽ የማድረግ ሥራውን በቀጣይነት እንደሚያጠናክር አስታውቋል።
3 days ago
🚨 አፋልጉኝ 🚨
ታዳጊ አልዓዛር ጌታቸው የ14 ዓመት ታዳጊ ሲሆን፣ ሰኔ 25 ቀን 2018 ዓ.ም. ከሚኖርበት ሐያት 49 ኮንዶሚኒየም እንደወጣ እስከ አሁን አልተመለሰም።
ያያችሁት ወይም ያለበትን ቦታ የምታውቁ አባካችሁ በሚከተሉት የስልክ ቁጥሮች በመደወል ለቤተሰቦቹ ጥቆማ በመስጠት ተባበሩ፡
📞 0911793976
📞 0991693268
ታዳጊ አልዓዛር ጌታቸው የ14 ዓመት ታዳጊ ሲሆን፣ ሰኔ 25 ቀን 2018 ዓ.ም. ከሚኖርበት ሐያት 49 ኮንዶሚኒየም እንደወጣ እስከ አሁን አልተመለሰም።
ያያችሁት ወይም ያለበትን ቦታ የምታውቁ አባካችሁ በሚከተሉት የስልክ ቁጥሮች በመደወል ለቤተሰቦቹ ጥቆማ በመስጠት ተባበሩ፡
📞 0911793976
📞 0991693268
4 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የሚኒያፖሊስ ፖሊስ ዲፓርትመንት የጠፉ ሁለት ታዳጊ ሴቶችን አድራሻ ለማግኘት እንዲረዳው የህብረተሰቡን ትብብር እየጠየቀ ይገኛል። ሁለቱ ታዳጊዎች አብረው እንዳሉ ተገምቷል።
የመጀመሪያዋ ታዳጊ የ14 ዓመቷ ሪሃና ዑስማን ስትሆን፣ ከጁላይ 23 ጀምሮ የጠፋች መሆኗ ተነግሯል። ሪሃና ቁመቷ 5 ጫማ ከ 5 ኢንች፣ ክብደቷ 150 ፓውንድ ሲሆን፣ ቀይ ጸጉር እና ቡናማ አይን ያላት፣ እንዲሁም አፍንጫዋን እና ጆሮዋን የተበሳች ናት። ለመጨረሻ ጊዜ ስትታይ አረንጓዴ ሹራብ፣ እንዲሁም ከኋላው "Ed Hardy" የሚል ጽሁፍ ያለው ቡናማ ሱሪ ለብሳ ነበር። በተጨማሪም ሪሃና በአሁኑ ወቅት በየቀኑ መውሰድ ያለባትን እና ጥገኛ የሆነችበትን አስፈላጊ መድሃኒት እያገኘች እንዳልሆነ የፖሊስ ባለስልጣናት አሳስበዋል።
ሁለተኛዋ ታዳጊ የ15 ዓመቷ አይሻ አህመድ ከጁላይ 31 ጀምሮ የጠፋች ሲሆን፣ ፖሊስ አይሻ ከሪሃና ጋር አብራ እንዳለች ያምናል። አይሻ ቁመቷ 5 ጫማ ከ 6 ኢንች፣ ክብደቷ 156 ፓውንድ፣ እንዲሁም ጥቁር ጸጉር እና ቡናማ አይን ያላት ታዳጊ ናት።
ማንኛውም ግለሰብ ስለነዚህ ታዳጊዎች ያሉበት ቦታ መረጃ ካለው፣ የሚኒያፖሊስ ፖሊስ ዲፓርትመንትን በስልክ ቁጥር 612-348-2345 ወይም በአስቸኳይ ጊዜ ስልክ 911 በመደወል ጥቆማ እንዲሰጥ ፖሊስ ጥሪውን አስተላልፏል። #minnesota
የመጀመሪያዋ ታዳጊ የ14 ዓመቷ ሪሃና ዑስማን ስትሆን፣ ከጁላይ 23 ጀምሮ የጠፋች መሆኗ ተነግሯል። ሪሃና ቁመቷ 5 ጫማ ከ 5 ኢንች፣ ክብደቷ 150 ፓውንድ ሲሆን፣ ቀይ ጸጉር እና ቡናማ አይን ያላት፣ እንዲሁም አፍንጫዋን እና ጆሮዋን የተበሳች ናት። ለመጨረሻ ጊዜ ስትታይ አረንጓዴ ሹራብ፣ እንዲሁም ከኋላው "Ed Hardy" የሚል ጽሁፍ ያለው ቡናማ ሱሪ ለብሳ ነበር። በተጨማሪም ሪሃና በአሁኑ ወቅት በየቀኑ መውሰድ ያለባትን እና ጥገኛ የሆነችበትን አስፈላጊ መድሃኒት እያገኘች እንዳልሆነ የፖሊስ ባለስልጣናት አሳስበዋል።
ሁለተኛዋ ታዳጊ የ15 ዓመቷ አይሻ አህመድ ከጁላይ 31 ጀምሮ የጠፋች ሲሆን፣ ፖሊስ አይሻ ከሪሃና ጋር አብራ እንዳለች ያምናል። አይሻ ቁመቷ 5 ጫማ ከ 6 ኢንች፣ ክብደቷ 156 ፓውንድ፣ እንዲሁም ጥቁር ጸጉር እና ቡናማ አይን ያላት ታዳጊ ናት።
ማንኛውም ግለሰብ ስለነዚህ ታዳጊዎች ያሉበት ቦታ መረጃ ካለው፣ የሚኒያፖሊስ ፖሊስ ዲፓርትመንትን በስልክ ቁጥር 612-348-2345 ወይም በአስቸኳይ ጊዜ ስልክ 911 በመደወል ጥቆማ እንዲሰጥ ፖሊስ ጥሪውን አስተላልፏል። #minnesota
Sponsored by
Surafel
4 days ago
(ዘ-ሐበሻ ስፖርት) ክሪስቶስ ቶሊስ ለመድፈኞቹ ባደረገው የመጀመሪያ የቅድመ-ውድድር ዘመን ጨዋታ ግብ በማስቆጠር፣ የአርሰናል ደጋፊዎች በቀጣዩ የውድድር ዘመን ከእርሱ ምን ሊጠብቁ እንደሚችሉ አስደሳች ፍንጭ ሰጥቷል። አርሰናል የስፔኑን ክለብ ጅሮናን 4 ለ 1 ባሸነፈበት በዚህ የመክፈቻ የአቋም መፈተሻ ጨዋታ፣ አዲሱ ፈራሚ ድንቅ እንቅስቃሴ አሳይቷል። ወደ ቤሺክታሽ ያቀናውን ሊያንድሮ ትሮሳርድን ለመተካት ከቤልጂየሙ ክለብ ክለብ ብሩጅ በ34 ሚሊዮን ፓውንድ የዝውውር ሂሳብ ወደ ሰሜን ለንደን ያመራው የ24 ዓመቱ ግሪካዊው ኢንተርናሽናል፣ በ30ኛው ደቂቃ ላይ አርናው ማርቲኔዝን በሚያምር ሁኔታ በማለፍ መሬት ለመሬት የመታው ኳስ ተከላካይ ታክኮ መረብ ላይ አርፏል።
ከዚህች ግብ 14 ደቂቃዎች አስቀድሞ የሚኬል አርቴታውን ስብስብ ቀዳሚ ያደረገችውን የመጀመሪያ ግብ ያስቆጠረው ጀርመናዊው አጥቂ ካይ ሃቨርትዝ ነበር። የ16 ዓመቱ ታዳጊ ማክስ ዶውማን ተከላካዮችን ሰንጥቆ ያቀበለውን ማራኪ ኳስ፣ ሃቨርትዝ ከጅሮናው ግብ ጠባቂ ፓውሎ ጋዛኒጋ ጋር ፊት ለፊት ተገናኝቶ በእርጋታ ወደ ግብነት ቀይሮታል።
ከእረፍት መልስ በ49ኛው ደቂቃ ላይ የጅሮናው ማርቲኔዝ ከማዕዘን የተሻገረለትን ኳስ ከፍ ብሎ በግንባሩ ገጭቶ በማስቆጠር የግብ ልዩነቱን ማጥበብ ቢችልም፣ ደስታቸው ግን ከሶስት ደቂቃዎች በላይ አልዘለቀም። ድንቁ ታዳጊ ዶውማን ወዲያውኑ የአርሰናልን የሁለት ግብ መሪነት መልሶ አረጋግጧል። የጎል ዝናቡ በዚህ ያላበቃ ሲሆን፣ ገብርኤል ጄሱስ በአምስት ደቂቃዎች ልዩነት ውስጥ ሌላ ግብ ከመረብ በማዋሃድ መድፈኞቹን 4 ለ 1 በሆነ ሰፊ ውጤት አሸናፊ ማድረግ ችሏል።
አርቴታ በስፔኑ ግጥሚያ ጠንካራ ቋሚ አሰላለፍ ይዘው ወደ ሜዳ የገቡ ሲሆን፣ ከዓለም ዋንጫ ተሳትፎ የተመለሱት ቪክቶር ጂዮክሬስ፣ ሃቨርትዝ እና ፒዬሮ ሂንካፒ እያንዳንዳቸው ለ30 ደቂቃዎች ያህል በሜዳ ላይ አሳልፈዋል። አርሰናል ሁለተኛውን የቅድመ-ውድድር ዘመን የአቋም መፈተሻ ጨዋታውን ለማድረግ ወደ ደብሊን የሚያመራ ሲሆን፣ በቀጣዩ ኦገስት 5 በአቪቫ ስታዲየም ከሪያል ቤቲስ ጋር ይፋለማል።
ከዚህች ግብ 14 ደቂቃዎች አስቀድሞ የሚኬል አርቴታውን ስብስብ ቀዳሚ ያደረገችውን የመጀመሪያ ግብ ያስቆጠረው ጀርመናዊው አጥቂ ካይ ሃቨርትዝ ነበር። የ16 ዓመቱ ታዳጊ ማክስ ዶውማን ተከላካዮችን ሰንጥቆ ያቀበለውን ማራኪ ኳስ፣ ሃቨርትዝ ከጅሮናው ግብ ጠባቂ ፓውሎ ጋዛኒጋ ጋር ፊት ለፊት ተገናኝቶ በእርጋታ ወደ ግብነት ቀይሮታል።
ከእረፍት መልስ በ49ኛው ደቂቃ ላይ የጅሮናው ማርቲኔዝ ከማዕዘን የተሻገረለትን ኳስ ከፍ ብሎ በግንባሩ ገጭቶ በማስቆጠር የግብ ልዩነቱን ማጥበብ ቢችልም፣ ደስታቸው ግን ከሶስት ደቂቃዎች በላይ አልዘለቀም። ድንቁ ታዳጊ ዶውማን ወዲያውኑ የአርሰናልን የሁለት ግብ መሪነት መልሶ አረጋግጧል። የጎል ዝናቡ በዚህ ያላበቃ ሲሆን፣ ገብርኤል ጄሱስ በአምስት ደቂቃዎች ልዩነት ውስጥ ሌላ ግብ ከመረብ በማዋሃድ መድፈኞቹን 4 ለ 1 በሆነ ሰፊ ውጤት አሸናፊ ማድረግ ችሏል።
አርቴታ በስፔኑ ግጥሚያ ጠንካራ ቋሚ አሰላለፍ ይዘው ወደ ሜዳ የገቡ ሲሆን፣ ከዓለም ዋንጫ ተሳትፎ የተመለሱት ቪክቶር ጂዮክሬስ፣ ሃቨርትዝ እና ፒዬሮ ሂንካፒ እያንዳንዳቸው ለ30 ደቂቃዎች ያህል በሜዳ ላይ አሳልፈዋል። አርሰናል ሁለተኛውን የቅድመ-ውድድር ዘመን የአቋም መፈተሻ ጨዋታውን ለማድረግ ወደ ደብሊን የሚያመራ ሲሆን፣ በቀጣዩ ኦገስት 5 በአቪቫ ስታዲየም ከሪያል ቤቲስ ጋር ይፋለማል።
5 days ago
ከጋብቻ ውጭ የወለደችውን ልጅ በወላጆቿ ግቢ ውስጥ በድብቅ የቀበረችው ግለሰብ በእስራት ተቀጣች
በቡኖ በደሌ ዞን ጮራ ወረዳ ውስጥ ከጋብቻ ውጭ በጤና ተቋም በሰላም የተገላገለችውን ልጅ ወላጆቿ ግቢ ውስጥ በድብቅ የቀበረችው ግለሰብ በእስራት ተቀጥታለች።
የጮራ ወረዳ ፖሊስ ፅ/ቤት የወንጀል ምርመራ ክፍል ኃላፊ ኢንስፔክተር በለጠ ጉታ ለብስራት ሬዲዮ እንደገለጹት ተከሳሽ ሙሚሻ ሱልጣን የአስራ ዘጠኝ አመት ታዳጊ ወጣት መሆኗን ገልጸዋል።
ግንቦት 5 ቀን 2018 ዓ.ም ከምሽቱ ሶስት ሰዓት ላይ በሰላም ከጤና ጣቢያ ልጇን ተገላግላ ወደ ቤት ስትገባ ወላጆቿ ከጋብቻ ውጭ በመውለዷ ባደረሱባት ቁጣ ተፅዕኖ ስር ወድቃ በነጋታው አስር ሰዓት ላይ የወለደችውን ጨቅላ ወንድ ልጅ አፍና ገድላዋለች። አስክሬኑን ካርቶን ውስጥ ሸሽጋ በማቆየት ምሽት ሶስት ሰዓት ላይ ማንም ሳያያት ልትቀብር ስትል በአካባቢው ማህረሰብ ጥቆማ መሰረት በፖሊስ ቁጥጥር ስር ውላለች።
የአራስ ልጇን አስክሬን ወደ ደልቢ ጤና ጣቢያ በመላክ ተከሳሿ ላይ አስፈላጊውን የምርመራ መዝገብ በሰውና በሕክምና ማስረጃ በማጠናከር ለአቃቢ ህግ ተላልፏል። አቃቢ ህግም ከፖሊስ የቀረበውን መዝገብ ተመልክቶ በህፃን መግደል ወንጀል ክስ መስርቶባታል።
በአቃቢ ህግ የተመሰረተውን ክስ የተመለከተው የቡኖ በደሌ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ሀምሌ 20 ቀን 2018 ዓ.ም በዋለው ችሎት ተከሳሿ አስባ የፈፀመችው የወንጀል ድርጊት በመሆኑ በአስራ አምስት አመት እስራት እንድትቀጣ የወሰነባት መሆኑን ኢንስፔክተር በለጠ ጨምረው ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል።
Seledadotio
Seledadotio
በቡኖ በደሌ ዞን ጮራ ወረዳ ውስጥ ከጋብቻ ውጭ በጤና ተቋም በሰላም የተገላገለችውን ልጅ ወላጆቿ ግቢ ውስጥ በድብቅ የቀበረችው ግለሰብ በእስራት ተቀጥታለች።
የጮራ ወረዳ ፖሊስ ፅ/ቤት የወንጀል ምርመራ ክፍል ኃላፊ ኢንስፔክተር በለጠ ጉታ ለብስራት ሬዲዮ እንደገለጹት ተከሳሽ ሙሚሻ ሱልጣን የአስራ ዘጠኝ አመት ታዳጊ ወጣት መሆኗን ገልጸዋል።
ግንቦት 5 ቀን 2018 ዓ.ም ከምሽቱ ሶስት ሰዓት ላይ በሰላም ከጤና ጣቢያ ልጇን ተገላግላ ወደ ቤት ስትገባ ወላጆቿ ከጋብቻ ውጭ በመውለዷ ባደረሱባት ቁጣ ተፅዕኖ ስር ወድቃ በነጋታው አስር ሰዓት ላይ የወለደችውን ጨቅላ ወንድ ልጅ አፍና ገድላዋለች። አስክሬኑን ካርቶን ውስጥ ሸሽጋ በማቆየት ምሽት ሶስት ሰዓት ላይ ማንም ሳያያት ልትቀብር ስትል በአካባቢው ማህረሰብ ጥቆማ መሰረት በፖሊስ ቁጥጥር ስር ውላለች።
የአራስ ልጇን አስክሬን ወደ ደልቢ ጤና ጣቢያ በመላክ ተከሳሿ ላይ አስፈላጊውን የምርመራ መዝገብ በሰውና በሕክምና ማስረጃ በማጠናከር ለአቃቢ ህግ ተላልፏል። አቃቢ ህግም ከፖሊስ የቀረበውን መዝገብ ተመልክቶ በህፃን መግደል ወንጀል ክስ መስርቶባታል።
በአቃቢ ህግ የተመሰረተውን ክስ የተመለከተው የቡኖ በደሌ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ሀምሌ 20 ቀን 2018 ዓ.ም በዋለው ችሎት ተከሳሿ አስባ የፈፀመችው የወንጀል ድርጊት በመሆኑ በአስራ አምስት አመት እስራት እንድትቀጣ የወሰነባት መሆኑን ኢንስፔክተር በለጠ ጨምረው ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል።
Seledadotio
Seledadotio
5 days ago
የስዊድን ፖሊስ በሀገሩ ስለጠፉት ኢትዮጵያውያን ምን አለ?
#ethiopia | በስዊድን ጎተንበርግ በተካሄደው የ2026 የጎቲያ ካፕ የዓለም አቀፍ የታዳጊዎች እግር ኳስ ውድድር ላይ ከተሳተፉ በኋላ ደብዛቸው የጠፋው ኢትዮጵያውያን ታዳጊዎች በገዛ ፈቃዳቸው መሄዳቸውንና በጉዳዩ ላይ ምንም ዓይነት የወንጀል ወይም የሰው ህገወጥ ዝውውር ምልክት እንዳልተገኘ የስዊድን ፖሊስ አስታወቀ።
ከሀምሌ 12 እስከ 18 በተካሄደው በዚህ ውድድር ላይ ሲሳተፉ የቆዩትና ዕድሜያቸው ከ14 እስከ 17 ዓመት የሚሆኗቸው አብዛኞቹ ታዳጊዎች ከአንድ አዋቂ የቡድን መሪያቸው ጋር በድምሩ ወደ 20 የሚጠጉ የቡድኑ አባላት ያረፉበትን ትምህርት ቤት ለቀው የተሰወሩት በውድድሩ የመጨረሻ ቀን ነበር።
የውድድሩ አዘጋጆች ቡድኑ ማደሪያውን ያለ ምንም ቅድመ ማሳወቂያ ለቆ መሄዱን ከተረዱ በኋላ ወዲያውኑ ለፖሊስ ጥቆማ ማድረሳቸው ታውቋል።
የስዊድን ፖሊስ ከአስፈላጊ አካላት ጋር በመተባበር የቡድኑ አባላት ያሉበትን አድራሻ ለማወቅ ጥረቱን የቀጠለ ሲሆን እስካሁን ግን ምንም ዓይነት ሕገ-ወጥ ድርጊት ስለመፈጸሙ የሚያሳይ ማስረጃ እንደሌለ ገልጿል።
የኢትዮጵያው ክለብ ተወካይ ተጫዋቾቹ በደህና ሁኔታ ላይ እንደሚገኙና ከቤተሰቦቻቸው ጋር መገናኘታቸውን ለስዊድን መገናኛ ብዙኃን የገለጹ ቢሆንም፣ በአሁኑ ወቅት ያሉበትን ትክክለኛ ቦታ ወይም ወደ ኢትዮጵያ መመለሳቸውን ግን ከማረጋገጥ ተቆጥበዋል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ባወጣው መግለጫ በክስተቱ ማዘኑን ገልጾ ቡድኑ በራሱ መንገድ ባመቻቸው ጉዞ የተሳተፈ እንጂ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድንን ወክሎ እንዳልተጓዘ አብራርቷል።
አክሎም ህዝቡ ታዳጊዎቹ የብሔራዊ ቡድን አባላት እንደሆኑ አድርገው የሚያቀርቡ የተሳሳቱ ዘገባዎችን እንዳይቀበል አሳስቧል።
በያፌት ገ/ህይወት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#ethiopia | በስዊድን ጎተንበርግ በተካሄደው የ2026 የጎቲያ ካፕ የዓለም አቀፍ የታዳጊዎች እግር ኳስ ውድድር ላይ ከተሳተፉ በኋላ ደብዛቸው የጠፋው ኢትዮጵያውያን ታዳጊዎች በገዛ ፈቃዳቸው መሄዳቸውንና በጉዳዩ ላይ ምንም ዓይነት የወንጀል ወይም የሰው ህገወጥ ዝውውር ምልክት እንዳልተገኘ የስዊድን ፖሊስ አስታወቀ።
ከሀምሌ 12 እስከ 18 በተካሄደው በዚህ ውድድር ላይ ሲሳተፉ የቆዩትና ዕድሜያቸው ከ14 እስከ 17 ዓመት የሚሆኗቸው አብዛኞቹ ታዳጊዎች ከአንድ አዋቂ የቡድን መሪያቸው ጋር በድምሩ ወደ 20 የሚጠጉ የቡድኑ አባላት ያረፉበትን ትምህርት ቤት ለቀው የተሰወሩት በውድድሩ የመጨረሻ ቀን ነበር።
የውድድሩ አዘጋጆች ቡድኑ ማደሪያውን ያለ ምንም ቅድመ ማሳወቂያ ለቆ መሄዱን ከተረዱ በኋላ ወዲያውኑ ለፖሊስ ጥቆማ ማድረሳቸው ታውቋል።
የስዊድን ፖሊስ ከአስፈላጊ አካላት ጋር በመተባበር የቡድኑ አባላት ያሉበትን አድራሻ ለማወቅ ጥረቱን የቀጠለ ሲሆን እስካሁን ግን ምንም ዓይነት ሕገ-ወጥ ድርጊት ስለመፈጸሙ የሚያሳይ ማስረጃ እንደሌለ ገልጿል።
የኢትዮጵያው ክለብ ተወካይ ተጫዋቾቹ በደህና ሁኔታ ላይ እንደሚገኙና ከቤተሰቦቻቸው ጋር መገናኘታቸውን ለስዊድን መገናኛ ብዙኃን የገለጹ ቢሆንም፣ በአሁኑ ወቅት ያሉበትን ትክክለኛ ቦታ ወይም ወደ ኢትዮጵያ መመለሳቸውን ግን ከማረጋገጥ ተቆጥበዋል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ባወጣው መግለጫ በክስተቱ ማዘኑን ገልጾ ቡድኑ በራሱ መንገድ ባመቻቸው ጉዞ የተሳተፈ እንጂ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድንን ወክሎ እንዳልተጓዘ አብራርቷል።
አክሎም ህዝቡ ታዳጊዎቹ የብሔራዊ ቡድን አባላት እንደሆኑ አድርገው የሚያቀርቡ የተሳሳቱ ዘገባዎችን እንዳይቀበል አሳስቧል።
በያፌት ገ/ህይወት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
6 days ago
የባለ ብዙ ወገን ዲፕሎማሲ - ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 23፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅሟን መሰረት ያደረገ እና ባለብዙ ወገን የውጭ ግንኙነት መርህን በመከተል አማራጮቿን እያሰፋች ትገኛለች።
ሀገሪቱ ለአንድ ወገን ባደላ አካሄድ ሳይሆን ብሔራዊ ጥቅሟን ሊያስከብሩ ከሚችሉ ወገኖች ሁሉ የጋራ ተጠቃሚነትን የጠበቀ ግንኙነት የመመስረት አቋም አላት።
ይህም አቋሟ በሀገራት መካከል ልዩነቶች ተፈጥረው ግንኙነታቸው ቢሻክርም ከሁለቱም ተቃራኒ ወገኖች ጋር ወዳጅነቷን አቻችላ ለመቀጠል አስችሏታል።
ኢትዮጵያ ከሌሎች ሀገራት ጋር በሚኖራት ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት "እኔ ብቻ ልጠቀም" የሚል መንገድ ሳትከተል የጋራ ተጠቃሚነትን ማዕከል አድርጋ ትንቀሳቀሳለች።
ከጎረቤት ሀገራት ጋር በጋራ የማደግ ፍላጎት ያላት ኢትዮጵያ፤ የተፈጥሮ የውሃ ሀብቶቿን ለመጠቀም ስታቅድም ሌሎችን ሳይጎዳ ጥንቃቄ በተሞላበት መንገድ ፍትሐዊ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ ትሰራለች።
ከዚህ ባለፈም የቀጣናው ሰላም እና ደህንነት እንዲጠበቅ ሰራዊቷን በማሰማራት ረገድ የጎላ ሚና ስታበረክት ቆይታለች።
ኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅሟን ለማስከበር ከወሰደቻቸው ርምጃዎች መካከል የብሪክስ ስብስብ አባል መሆኗ አንዱ ነው። ይህ አባልነቷ ከምዕራባውያን ሀገራት ጋር ያላትን ግንኙነት በጠበቀ መልኩ የተከናወነ ሲሆን፤ ይህም ሀገሪቱ ለጋራ ጥቅም በጋራ የመስራት ቁርጠኝነቷ ማሳያ ነው።
የብሪክስ አባልነት ታዳጊ ሀገራት ያላቸውን የድምፅ መስጠት አቅም ይጨምራል፤ የወጪ ንግድ አቅምን ለማሳደግና ኢንቨስትመንትን ለመሳብ እድል ከመስጠት ባሻገር የውጭ ምንዛሪ እጥረትን ለመፍታት ያግዛል፡፡
በተጨማሪም በሀገራቱ መካከል የእውቀት ልውውጦች እንዲፈጠሩ፣ ደህንነት በተመለከቱ ጉዳዮች ላይ በጋራ መስራት እንዲቻል፤ እንዲሁም እርስ በርስ ያሉ ግንኙነቶችን ለማሳደግ ዕድል ይፈጥራል።
በቤተልሔም ግርማ
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 23፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅሟን መሰረት ያደረገ እና ባለብዙ ወገን የውጭ ግንኙነት መርህን በመከተል አማራጮቿን እያሰፋች ትገኛለች።
ሀገሪቱ ለአንድ ወገን ባደላ አካሄድ ሳይሆን ብሔራዊ ጥቅሟን ሊያስከብሩ ከሚችሉ ወገኖች ሁሉ የጋራ ተጠቃሚነትን የጠበቀ ግንኙነት የመመስረት አቋም አላት።
ይህም አቋሟ በሀገራት መካከል ልዩነቶች ተፈጥረው ግንኙነታቸው ቢሻክርም ከሁለቱም ተቃራኒ ወገኖች ጋር ወዳጅነቷን አቻችላ ለመቀጠል አስችሏታል።
ኢትዮጵያ ከሌሎች ሀገራት ጋር በሚኖራት ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት "እኔ ብቻ ልጠቀም" የሚል መንገድ ሳትከተል የጋራ ተጠቃሚነትን ማዕከል አድርጋ ትንቀሳቀሳለች።
ከጎረቤት ሀገራት ጋር በጋራ የማደግ ፍላጎት ያላት ኢትዮጵያ፤ የተፈጥሮ የውሃ ሀብቶቿን ለመጠቀም ስታቅድም ሌሎችን ሳይጎዳ ጥንቃቄ በተሞላበት መንገድ ፍትሐዊ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ ትሰራለች።
ከዚህ ባለፈም የቀጣናው ሰላም እና ደህንነት እንዲጠበቅ ሰራዊቷን በማሰማራት ረገድ የጎላ ሚና ስታበረክት ቆይታለች።
ኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅሟን ለማስከበር ከወሰደቻቸው ርምጃዎች መካከል የብሪክስ ስብስብ አባል መሆኗ አንዱ ነው። ይህ አባልነቷ ከምዕራባውያን ሀገራት ጋር ያላትን ግንኙነት በጠበቀ መልኩ የተከናወነ ሲሆን፤ ይህም ሀገሪቱ ለጋራ ጥቅም በጋራ የመስራት ቁርጠኝነቷ ማሳያ ነው።
የብሪክስ አባልነት ታዳጊ ሀገራት ያላቸውን የድምፅ መስጠት አቅም ይጨምራል፤ የወጪ ንግድ አቅምን ለማሳደግና ኢንቨስትመንትን ለመሳብ እድል ከመስጠት ባሻገር የውጭ ምንዛሪ እጥረትን ለመፍታት ያግዛል፡፡
በተጨማሪም በሀገራቱ መካከል የእውቀት ልውውጦች እንዲፈጠሩ፣ ደህንነት በተመለከቱ ጉዳዮች ላይ በጋራ መስራት እንዲቻል፤ እንዲሁም እርስ በርስ ያሉ ግንኙነቶችን ለማሳደግ ዕድል ይፈጥራል።
በቤተልሔም ግርማ
7 days ago
(ዘ-ሐበሻ ስፖርት) እግር ኳስ አንዳንዴ ከስፖርትነት አልፎ ድንቅ እና ስሜት ቀስቃሽ ታሪኮችን ይጽፋል። የ8 ወር ህጻን እያለ በሀገሩ ሄይቲ በደረሰው እና ከ300 ሺህ በላይ ሰዎችን ህይወት በከፋ ሁኔታ በቀጠፈው አሰቃቂ የመሬት መንቀጥቀጥ ወቅት፣ ከተአምር በተጠጋ ሁኔታ የተረፈው ወጣት፤ ዛሬ በዓለም እግር ኳስ ታላቁን ሰማያዊ እና ነጭ ማሊያ ለብሶ አዲስ ታሪክ ጽፏል።
የ17 ዓመቱ ስቲቨን "ኪኪ" ራሞስ ለአርጀንቲና ከ17 ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድን በመሰለፍ፣ በሄይቲ ተወልዶ የታላቋን ደቡብ አሜሪካ ሀገር ማሊያ የለበሰ የመጀመሪያው ተጫዋች መሆን ችሏል!
በታዋቂው የቬሌዝ ሳርስፊልድ አካዳሚ ውስጥ በክንፍ አጥቂነት የሚያበራው ይህ ታዳጊ፣ አርጀንቲና ኢኳዶርን 2ለ1 ባሸነፈችበት ጨዋታ ላይ ለአልቢሴሌስቴዎች የመጀመሪያ ጨዋታውን አድርጓል። በጨዋታው ላይ ድንቅ እንቅስቃሴ በማሳየት እና ሁለት ግቦችን በማስቆጠር ቡድኑን ለድል ያበቃው ኪኪ ራሞስ፣ በዓለም እግር ኳስ ግዙፍ ስም ባላቸው አርጀንቲናውያን ዘንድ ስሙን በወርቅ ቀለም ጽፏል።
በ2009 በፖርት-ኦ-ፕሪንስ ሄይቲ የተወለደው ኪኪ፣ ለአርጀንቲና በማንኛውም የዕድሜ እርከን ብሔራዊ ቡድን ውስጥ የተሰለፈ የመጀመሪያው በሄይቲ የተወለደ ጥቁር ተጫዋች በመሆን አዲስ የኢንተርናሽናል እግር ኳስ ምዕራፍ ከፍቷል።
የኪኪ የህይወት ታሪክ ልክ እንደ አስደናቂ የፊልም ስክሪፕት ነው። እ.ኤ.አ በ2010 በሄይቲ ደርሶ በነበረው አውዳሚ የመሬት መንቀጥቀጥ ወቅት ገና የ8 ወር ህጻን የነበረው ኪኪ፣ በነበረበት የሕፃናት ማደሪያ ጣቢያ ውስጥ ጉዳት ሳይደርስበት ከተረፉት በጣም ጥቂት ህጻናት አንዱ ነበር።
ባዮሎጂካል ወላጆቹ አርጀንቲናውያን ባይሆኑም፣ አንድ ደግ ልብ ያላቸው አርጀንቲናውያን ባልና ሚስት በጉዲፈቻ ወስደው ወደ ቦነስ አይረስ አመጡት። ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ህይወቱን ሙሉ በአርጀንቲና ያሳለፈው፣ ቋንቋውን እና ባህሉን ለምዶ ያደገው ኪኪ፣ የሀገሪቱን ዜግነት በመያዝ ለብሔራዊ ቡድኑ የመጫወት ህጋዊ መብትን አግኝቷል።
የኪኪ ራሞስ ታሪክ ይፋ መሆንን ተከትሎ በአርጀንቲናውያን የእግር ኳስ አፍቃሪዎች ዘንድ ከፍተኛ ደስታ እና ኩራት ተፈጥሯል። በጨዋታው ካሳየው ከፍተኛ ተሰጥኦ ባሻገር፣ ከሞት አፍ ወጥቶ ለአርጀንቲና ማሊያ እስከመበቃት ያደረገውን ተአምራዊ ጉዞ የተመለከቱ የስፖርቱ ተከታታዮች፣ "እግር ኳስ ሰዎችን የሚያስተስርር ድንቅ ድልድይ ነው" ሲሉ አድናቆታቸውን ገልጸዋል።
ገና በ17 ዓመቱ በአርጀንቲና እግር ኳስ ታሪክ ውስጥ ልዩ ቦታ የያዘው ይህ ፈጣን የክንፍ መስመር ተጫዋች፣ በቀጣይ በታላቁ የአርጀንቲና ዋና ብሔራዊ ቡድን ውስጥ የመሰለፍ ህልሙን ያሳካ ይሆን? የዓለም እግር ኳስ አፍቃሪዎች ከወዲሁ የዚህን ድንቅ ወጣት ቀጣይ እርምጃዎች በትልቅ ጉጉት እየተከታተሉ ይገኛሉ።
የ17 ዓመቱ ስቲቨን "ኪኪ" ራሞስ ለአርጀንቲና ከ17 ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድን በመሰለፍ፣ በሄይቲ ተወልዶ የታላቋን ደቡብ አሜሪካ ሀገር ማሊያ የለበሰ የመጀመሪያው ተጫዋች መሆን ችሏል!
በታዋቂው የቬሌዝ ሳርስፊልድ አካዳሚ ውስጥ በክንፍ አጥቂነት የሚያበራው ይህ ታዳጊ፣ አርጀንቲና ኢኳዶርን 2ለ1 ባሸነፈችበት ጨዋታ ላይ ለአልቢሴሌስቴዎች የመጀመሪያ ጨዋታውን አድርጓል። በጨዋታው ላይ ድንቅ እንቅስቃሴ በማሳየት እና ሁለት ግቦችን በማስቆጠር ቡድኑን ለድል ያበቃው ኪኪ ራሞስ፣ በዓለም እግር ኳስ ግዙፍ ስም ባላቸው አርጀንቲናውያን ዘንድ ስሙን በወርቅ ቀለም ጽፏል።
በ2009 በፖርት-ኦ-ፕሪንስ ሄይቲ የተወለደው ኪኪ፣ ለአርጀንቲና በማንኛውም የዕድሜ እርከን ብሔራዊ ቡድን ውስጥ የተሰለፈ የመጀመሪያው በሄይቲ የተወለደ ጥቁር ተጫዋች በመሆን አዲስ የኢንተርናሽናል እግር ኳስ ምዕራፍ ከፍቷል።
የኪኪ የህይወት ታሪክ ልክ እንደ አስደናቂ የፊልም ስክሪፕት ነው። እ.ኤ.አ በ2010 በሄይቲ ደርሶ በነበረው አውዳሚ የመሬት መንቀጥቀጥ ወቅት ገና የ8 ወር ህጻን የነበረው ኪኪ፣ በነበረበት የሕፃናት ማደሪያ ጣቢያ ውስጥ ጉዳት ሳይደርስበት ከተረፉት በጣም ጥቂት ህጻናት አንዱ ነበር።
ባዮሎጂካል ወላጆቹ አርጀንቲናውያን ባይሆኑም፣ አንድ ደግ ልብ ያላቸው አርጀንቲናውያን ባልና ሚስት በጉዲፈቻ ወስደው ወደ ቦነስ አይረስ አመጡት። ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ህይወቱን ሙሉ በአርጀንቲና ያሳለፈው፣ ቋንቋውን እና ባህሉን ለምዶ ያደገው ኪኪ፣ የሀገሪቱን ዜግነት በመያዝ ለብሔራዊ ቡድኑ የመጫወት ህጋዊ መብትን አግኝቷል።
የኪኪ ራሞስ ታሪክ ይፋ መሆንን ተከትሎ በአርጀንቲናውያን የእግር ኳስ አፍቃሪዎች ዘንድ ከፍተኛ ደስታ እና ኩራት ተፈጥሯል። በጨዋታው ካሳየው ከፍተኛ ተሰጥኦ ባሻገር፣ ከሞት አፍ ወጥቶ ለአርጀንቲና ማሊያ እስከመበቃት ያደረገውን ተአምራዊ ጉዞ የተመለከቱ የስፖርቱ ተከታታዮች፣ "እግር ኳስ ሰዎችን የሚያስተስርር ድንቅ ድልድይ ነው" ሲሉ አድናቆታቸውን ገልጸዋል።
ገና በ17 ዓመቱ በአርጀንቲና እግር ኳስ ታሪክ ውስጥ ልዩ ቦታ የያዘው ይህ ፈጣን የክንፍ መስመር ተጫዋች፣ በቀጣይ በታላቁ የአርጀንቲና ዋና ብሔራዊ ቡድን ውስጥ የመሰለፍ ህልሙን ያሳካ ይሆን? የዓለም እግር ኳስ አፍቃሪዎች ከወዲሁ የዚህን ድንቅ ወጣት ቀጣይ እርምጃዎች በትልቅ ጉጉት እየተከታተሉ ይገኛሉ።
7 days ago
"18 ሰው ቀርቶብናል፥ እናትና ልጅም ይገኙበታል፥ ለአዘጋጆቹ ወዲያው አሳውቀናል" - የፕሮጀክቱ መስራች
ለጎቲያ ካፕ ወደ ስዊዲን ከሄዱ የኢትዮጵያ ቡድኖች መካከል ደብል ፓስ የእግር ኳስ ፕሮጀክት አንዱ ነው፤ ከቀሩት ተጫዋቾች አብዛኞቹ ከዚህ ስብስብስ የተገኙ በመሆናቸው ስለ ጉዳዩ ማብራሪያ እንዲሰጠን የፕሮጀክቱ መስራች ታዲዮስ ተክሉ ጋር ደውለን ተከታዩን ቆይታ አድርገናል፥ እነሆ፦
ታዲዮስ ስለ ትብብርህ በቅድሚያ እናመሰግናለን፤ ስለራስህና ስለ ፕሮጀክታችሁ በማስተዋወቅ እንጀምር እስኪ?
"ጉዳዩን ለማጥራት ስለደወልክልኝ ታምሩ እኔም አመሰግናለሁ፤ ታዲዮስ ተክሉ እባለሁ፤ የቀድሞ ተጫዋች የአሁን አሰልጣኝ ነኝ፤ ከጫካ ሜዳ ፕሮጀክት ጀምሮ የኢትዮጵያ ቡና፣ ንግድ ባንክና ኤሌክትሪክ ታዳጊ ቡድኖችን አሰልጥኛለሁ፤ የኢትዮጵያ ከ17 አመት በታች ብሄራዊ ቡድን አሰልጣኝ ሆኜም በሴካፋ ተሳትፌያለሁ፤ አሁን ደግሞ የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ሴቶች ቡድንን አሰለጥናለሁ፤ በተጨማሪ የደብል ፓስ ፕሮጀክት መስራችና ዋና አሰልጣኝ ነኝ፤ ይህ ፕሮጀክት ከተቋቋመ ዘጠኝ አመት ሆኖታል፤ በአዲስ አበባ እግርኳስ ፌዴሬሽን ስር ተመዝግበን በከተማው ከ20 አመት በታች ውድድር ላይ እንሳተፋለን"
የስዊዲን ጎቲያ ካፕ እድልን እንዴት አገኛችሁ?
"በራሳችን ጥረት ተፃፅፈን ነው እድሉን ያገኘነው፤ ዘንድሮ ለሁለተኛ ጊዜ ነው የተሳተፍነው፤ ከዚህ ቀደም ዴንማርክ ላይም ውድድር አድርገናል"
እስኪ ስለ ስዊዲን ጉዟችሁ አጫውተን
"18 ተጫዋቾችንና 4 የአሰልጣኝ አባላትን በጥቅሉ 22 ልዑካንን ይዘን ነው የሄድነው፤ በውድድሩም ጥሩ ተሳትፎ ነበረን"
22 ሆናችሁ ሄዳችሁ ስንት ሆናችሁ ተመለሳችሁ?
"1 ተጫዋች( የዘማሪ አሸናፊ ገብረ ማርያም ልጅ ፣ ሚካኤል አሸናፊ ) ና 3 የአሰልጣኝ አባላት በአጠቃላይ 4 ሰዎች ብቻ ነው ወደ አዲስ አበባ የተመለሰው፤ 18ቱ አልመጡም"
ይህ እንዴት ሊፈጠር ቻለ?
"የሁላችንም መመለሻ ቀን ውድድሩ ከተጠናቀቀ ከሁለት ቀን በኋላ ነበር፤ ሆኖም የአንዱ ታዳጊ ተጫዋች የቅርብ ቤተሰብ ሰርግ ሀምሌ 12 ስለነበር ወላጆቹ ቶሎ ቢመጣልን አሉን፤ በእድሜው ምክንያት ብቻውን መላክ ስለማንችል እኔና ሁለት የአሰልጣኝ አባላት እንዲሁም ተጫዋቹን ጨምሮ አራት ሆነን ትኬታችንን አስተካክለን በፍፃሜው ቀን ቅዳሜ ሀምሌ 11/2018(ጁላይ 18/2026) ወደ አዲስ አበባ ተመለስን፤ ቀሪዎቹ 18ቱ ሰኞ ሀምሌ 13 ነበር የመመለሻ ቀናቸው፤ እኛ አዲስ አበባ ሳንደርስ ለትራንዚት በቆየንበት ኳታር ሆነን ግን ተጫዋቾቹ ቡድናችን ካረፈበት ትምህርት ቤት ሳያሳውቁ እንደወጡ ተነገረን"
ከዛ ምን አደረጋችሁ?
"ወዲያው ለአዘጋጆቹ አሳወቅናቸው፤ እነሱም ለመረጃው አመስግነውን ለሚመለከተው የፀጥታ አካል እንሳውቃለን አሉን፤ አዲስ አበባ ከደረስን በኋላ ድጋሚ አንዷ የቡድን መሪ ጋር ስደውል እንደማይመለሱ፥ ተጫዋቾቹንም ስዊዲን የሚኖሩ ቤተሰብና ዘመዶቻቸው እንደወሰዷቸው ነገረችን፤ ኢትዮጵያ ያሉ ወላጆችንም ጠየቅን፤ ልጆቹ ያሉበትን ቦታ ለመናገር ፈቃደኛ አልሆኑም፤ ይህንንም ለአዘጋጆቹ በድጋሚ አሳውቀናል፤ ከ10 ቀን በኋላ ዜናውን አወጡት"
ይህ እንዳይከሰት ቅድሚያ ዝግጅት አላደረጋችሁም?
"በደንብ አድርገናል፤ ውል አዘጋጅተን የሁሉንም ተጫዋቾች ወላጆች አስፈርመናል፤ ስዊዲን ከደረስን በኋላም የሁሉም ተጫዋቾች ፓስፖርት እኔ ጋር ነበር፤ ሆኖም እኔ ቀድሜ መመለስ ስለነበረብኝ ፓስፖርቱን ለቡድን መሪ ሰጠሁ፤ ተያይዘው ቀሩ፤ ውስጥ ውስጡን በደንብ ተዘጋጅተውበት ነበር"
ለመሆኑ ወጪያችሁን የሸፈነው ማነው?
"የተጫዋቾቹን የጉዞ ወጪ የቻሉት ወላጆቻቸው ናቸው"
ምን ያህል ከፈሉ?
" ለስልጠና፣ ለጉዞና ለተለያዩ አቅርቦቶች እያንዳንዳቸው 300ሺህ ብር ከፍለዋል፤ የተሻለ አቅም ያላቸው ደግሞ 400ሺህ ብር ከፍለው አግዘውናል"
ለምን 400ሺህ ብር?
"የመክፈል አቅም የሌላቸውን ሶስት ያህል ተጫዋቾችን ይዘን ሄደናል፤ የእነሱን ወጪ ደግሞ እኛና አቅም ያላቸው ወላጆች ሸፍነናል፤ ወላጆቹ ከ300ሺህ ብር በተጨማሪ 100ሺህ ብር እየጨመሩ 400ሺህ ብር እየከፈሉ አቅም የሌላቸው ተጫዋቾች እንዲሄዱ አግዘውናል"
ከተጫዋቾች በተጨማሪ ወላጆችስ ሄደዋል?
"አዎ ሁለት ተጫዋቾች ከእናቶቻቸው ጋር አብረው ወደ ስዊዲን ሄደዋል"
እና ተመለሱ?
"ሁለቱም ተጫዋቾችም ሆኑ እናቶቻቸው አልተመለሱም"
ተጓዥ ተጫዋቾች ከእግርኳስ ጋር ያላቸው ግንኙነትና ችሎታ ደካማ የሆኑ፥ የባለሀብትና የባለስልጣን ልጆች ናቸው ይባላል እውነት ነው?
"ፕሮጀክታችን በኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽንና በፊፋ ኮኔክት የተመዘገበ ነው፤ ሆኖም እድሜያቸው ከ16 አመት በታች ስለሆኑ ችሎታ ላይ ብቻ የተመሰረተ ምልመላ አናደርግም፤ ይህን መሰል አለም አቀፍ ውድድር ላይ ስንሳተፍ ደግሞ ቪዛ ለማግኘት አንዱ መስፈርት የወላጆቹ ኢኮኖሚያዊ አቅም ይታያል፤ ስለዚህ የባለሀብትም የባለስልጣንም ልጆች ይኖሩናል፤ ከቀሩት ውስጥ ግን የባለስልጣን ልጅ የለም"
የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን በተጫዋቾቹ መጥፋት አዝኛለሁ ሆኖም የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን አባላት አይደሉም ብሎ መግለጫ አውጥቷል፤ ምን ትላለህ?
"እንዳልኩህ በራሳችን ጥረት ነው ተሳትፎውን ያገኘነው፤ ከብሄራዊ ቡድን ጋርም አይገናኝም፤ በተፈጠረው ነገር ዋነኛ ተጎጂዎችም እኛ ነን፤ ስማችን ላይ ትልቅ አሉታዊ ተፅዕኖ አለው፤ በጣም አዝነናል"
በድጋሚ ለትብብርህ ላመስግንህና የመጨረሻ ጥያቄ ላንሳ፥ የቡድኑ ፎቶ ላይ አንድ ህፃን ልጅ ይታያል፤ ተጫዋች ነው?
"ኸረ አይደለም፤ የእኔ ልጅ ነው፤ ገና ስድስት አመቱ ነው፤ አብረን ሄደን አብረን ተመልሰናል"
★ ማስታወሻ፦ ከደብል ፓስ ፕሮጀክት በተጨማሪ በአሰልጣኝ እድሉ ደረጄ የሚመራው ኢዲዋይ እና ዳን አቢሲኒያ የተባሉ ቡድኖች በስዊዲን ጎቲያ ካፕ ተሳትፈዋል፤ እነሱም ማብራሪያ እንዲሰጡን ጠይቀን ምላሻቸውን እየጠበቅን ነው
(ታምሩ ዓለሙ)
ለጎቲያ ካፕ ወደ ስዊዲን ከሄዱ የኢትዮጵያ ቡድኖች መካከል ደብል ፓስ የእግር ኳስ ፕሮጀክት አንዱ ነው፤ ከቀሩት ተጫዋቾች አብዛኞቹ ከዚህ ስብስብስ የተገኙ በመሆናቸው ስለ ጉዳዩ ማብራሪያ እንዲሰጠን የፕሮጀክቱ መስራች ታዲዮስ ተክሉ ጋር ደውለን ተከታዩን ቆይታ አድርገናል፥ እነሆ፦
ታዲዮስ ስለ ትብብርህ በቅድሚያ እናመሰግናለን፤ ስለራስህና ስለ ፕሮጀክታችሁ በማስተዋወቅ እንጀምር እስኪ?
"ጉዳዩን ለማጥራት ስለደወልክልኝ ታምሩ እኔም አመሰግናለሁ፤ ታዲዮስ ተክሉ እባለሁ፤ የቀድሞ ተጫዋች የአሁን አሰልጣኝ ነኝ፤ ከጫካ ሜዳ ፕሮጀክት ጀምሮ የኢትዮጵያ ቡና፣ ንግድ ባንክና ኤሌክትሪክ ታዳጊ ቡድኖችን አሰልጥኛለሁ፤ የኢትዮጵያ ከ17 አመት በታች ብሄራዊ ቡድን አሰልጣኝ ሆኜም በሴካፋ ተሳትፌያለሁ፤ አሁን ደግሞ የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ሴቶች ቡድንን አሰለጥናለሁ፤ በተጨማሪ የደብል ፓስ ፕሮጀክት መስራችና ዋና አሰልጣኝ ነኝ፤ ይህ ፕሮጀክት ከተቋቋመ ዘጠኝ አመት ሆኖታል፤ በአዲስ አበባ እግርኳስ ፌዴሬሽን ስር ተመዝግበን በከተማው ከ20 አመት በታች ውድድር ላይ እንሳተፋለን"
የስዊዲን ጎቲያ ካፕ እድልን እንዴት አገኛችሁ?
"በራሳችን ጥረት ተፃፅፈን ነው እድሉን ያገኘነው፤ ዘንድሮ ለሁለተኛ ጊዜ ነው የተሳተፍነው፤ ከዚህ ቀደም ዴንማርክ ላይም ውድድር አድርገናል"
እስኪ ስለ ስዊዲን ጉዟችሁ አጫውተን
"18 ተጫዋቾችንና 4 የአሰልጣኝ አባላትን በጥቅሉ 22 ልዑካንን ይዘን ነው የሄድነው፤ በውድድሩም ጥሩ ተሳትፎ ነበረን"
22 ሆናችሁ ሄዳችሁ ስንት ሆናችሁ ተመለሳችሁ?
"1 ተጫዋች( የዘማሪ አሸናፊ ገብረ ማርያም ልጅ ፣ ሚካኤል አሸናፊ ) ና 3 የአሰልጣኝ አባላት በአጠቃላይ 4 ሰዎች ብቻ ነው ወደ አዲስ አበባ የተመለሰው፤ 18ቱ አልመጡም"
ይህ እንዴት ሊፈጠር ቻለ?
"የሁላችንም መመለሻ ቀን ውድድሩ ከተጠናቀቀ ከሁለት ቀን በኋላ ነበር፤ ሆኖም የአንዱ ታዳጊ ተጫዋች የቅርብ ቤተሰብ ሰርግ ሀምሌ 12 ስለነበር ወላጆቹ ቶሎ ቢመጣልን አሉን፤ በእድሜው ምክንያት ብቻውን መላክ ስለማንችል እኔና ሁለት የአሰልጣኝ አባላት እንዲሁም ተጫዋቹን ጨምሮ አራት ሆነን ትኬታችንን አስተካክለን በፍፃሜው ቀን ቅዳሜ ሀምሌ 11/2018(ጁላይ 18/2026) ወደ አዲስ አበባ ተመለስን፤ ቀሪዎቹ 18ቱ ሰኞ ሀምሌ 13 ነበር የመመለሻ ቀናቸው፤ እኛ አዲስ አበባ ሳንደርስ ለትራንዚት በቆየንበት ኳታር ሆነን ግን ተጫዋቾቹ ቡድናችን ካረፈበት ትምህርት ቤት ሳያሳውቁ እንደወጡ ተነገረን"
ከዛ ምን አደረጋችሁ?
"ወዲያው ለአዘጋጆቹ አሳወቅናቸው፤ እነሱም ለመረጃው አመስግነውን ለሚመለከተው የፀጥታ አካል እንሳውቃለን አሉን፤ አዲስ አበባ ከደረስን በኋላ ድጋሚ አንዷ የቡድን መሪ ጋር ስደውል እንደማይመለሱ፥ ተጫዋቾቹንም ስዊዲን የሚኖሩ ቤተሰብና ዘመዶቻቸው እንደወሰዷቸው ነገረችን፤ ኢትዮጵያ ያሉ ወላጆችንም ጠየቅን፤ ልጆቹ ያሉበትን ቦታ ለመናገር ፈቃደኛ አልሆኑም፤ ይህንንም ለአዘጋጆቹ በድጋሚ አሳውቀናል፤ ከ10 ቀን በኋላ ዜናውን አወጡት"
ይህ እንዳይከሰት ቅድሚያ ዝግጅት አላደረጋችሁም?
"በደንብ አድርገናል፤ ውል አዘጋጅተን የሁሉንም ተጫዋቾች ወላጆች አስፈርመናል፤ ስዊዲን ከደረስን በኋላም የሁሉም ተጫዋቾች ፓስፖርት እኔ ጋር ነበር፤ ሆኖም እኔ ቀድሜ መመለስ ስለነበረብኝ ፓስፖርቱን ለቡድን መሪ ሰጠሁ፤ ተያይዘው ቀሩ፤ ውስጥ ውስጡን በደንብ ተዘጋጅተውበት ነበር"
ለመሆኑ ወጪያችሁን የሸፈነው ማነው?
"የተጫዋቾቹን የጉዞ ወጪ የቻሉት ወላጆቻቸው ናቸው"
ምን ያህል ከፈሉ?
" ለስልጠና፣ ለጉዞና ለተለያዩ አቅርቦቶች እያንዳንዳቸው 300ሺህ ብር ከፍለዋል፤ የተሻለ አቅም ያላቸው ደግሞ 400ሺህ ብር ከፍለው አግዘውናል"
ለምን 400ሺህ ብር?
"የመክፈል አቅም የሌላቸውን ሶስት ያህል ተጫዋቾችን ይዘን ሄደናል፤ የእነሱን ወጪ ደግሞ እኛና አቅም ያላቸው ወላጆች ሸፍነናል፤ ወላጆቹ ከ300ሺህ ብር በተጨማሪ 100ሺህ ብር እየጨመሩ 400ሺህ ብር እየከፈሉ አቅም የሌላቸው ተጫዋቾች እንዲሄዱ አግዘውናል"
ከተጫዋቾች በተጨማሪ ወላጆችስ ሄደዋል?
"አዎ ሁለት ተጫዋቾች ከእናቶቻቸው ጋር አብረው ወደ ስዊዲን ሄደዋል"
እና ተመለሱ?
"ሁለቱም ተጫዋቾችም ሆኑ እናቶቻቸው አልተመለሱም"
ተጓዥ ተጫዋቾች ከእግርኳስ ጋር ያላቸው ግንኙነትና ችሎታ ደካማ የሆኑ፥ የባለሀብትና የባለስልጣን ልጆች ናቸው ይባላል እውነት ነው?
"ፕሮጀክታችን በኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽንና በፊፋ ኮኔክት የተመዘገበ ነው፤ ሆኖም እድሜያቸው ከ16 አመት በታች ስለሆኑ ችሎታ ላይ ብቻ የተመሰረተ ምልመላ አናደርግም፤ ይህን መሰል አለም አቀፍ ውድድር ላይ ስንሳተፍ ደግሞ ቪዛ ለማግኘት አንዱ መስፈርት የወላጆቹ ኢኮኖሚያዊ አቅም ይታያል፤ ስለዚህ የባለሀብትም የባለስልጣንም ልጆች ይኖሩናል፤ ከቀሩት ውስጥ ግን የባለስልጣን ልጅ የለም"
የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን በተጫዋቾቹ መጥፋት አዝኛለሁ ሆኖም የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን አባላት አይደሉም ብሎ መግለጫ አውጥቷል፤ ምን ትላለህ?
"እንዳልኩህ በራሳችን ጥረት ነው ተሳትፎውን ያገኘነው፤ ከብሄራዊ ቡድን ጋርም አይገናኝም፤ በተፈጠረው ነገር ዋነኛ ተጎጂዎችም እኛ ነን፤ ስማችን ላይ ትልቅ አሉታዊ ተፅዕኖ አለው፤ በጣም አዝነናል"
በድጋሚ ለትብብርህ ላመስግንህና የመጨረሻ ጥያቄ ላንሳ፥ የቡድኑ ፎቶ ላይ አንድ ህፃን ልጅ ይታያል፤ ተጫዋች ነው?
"ኸረ አይደለም፤ የእኔ ልጅ ነው፤ ገና ስድስት አመቱ ነው፤ አብረን ሄደን አብረን ተመልሰናል"
★ ማስታወሻ፦ ከደብል ፓስ ፕሮጀክት በተጨማሪ በአሰልጣኝ እድሉ ደረጄ የሚመራው ኢዲዋይ እና ዳን አቢሲኒያ የተባሉ ቡድኖች በስዊዲን ጎቲያ ካፕ ተሳትፈዋል፤ እነሱም ማብራሪያ እንዲሰጡን ጠይቀን ምላሻቸውን እየጠበቅን ነው
(ታምሩ ዓለሙ)
7 days ago
ወደ ስዊድን ያቀኑ 20 የእግርኳስ ቡድን አባላት መጥፋታቸው ተሰማ
ወደ ስዊድን ያቀኑ ዕድሜያቸው ከ 14 እስከ 17 የሚገመት 20 ታዳጊ የእግርኳስ ተጫዋቾች ከ መሪያቸው ጋር መጥፋታቸውን ስዊድን ሄራልድ ዘግቧል።
"ጎቲያካፕ" ለተሰኘ የእግር ኳስ ውድድር ከኢትዮጵያ የሔዱት ታዳጊዎች ካረፉበት ትምሕርት ቤት ሳያሳውቁ በመውጣት መሰወራቸውን የስዊድን ፖሊስ አስታውቋል።እግር ኳስ ተጫዋቾቹ ወደ ኢትዮጵያ እንዳልተመለሱ ያረጋገጠው ፖሊስ፤ በራሳቸው ፍላጎት ጠፍተው ሊሆን እንደሚችል አመላክቷል።
በጉዳዩ ዙርያ ምላሽ የሰጠው ፌደሬሽኑ የቡድኑ አባላት መጥፋት እንዳሳዘነው እና ታዳጊዎቹ በመሰል ውድድሮች ላይ በራሳቸው ጥረት በሚያገኙት እድል ወደ ውድድሩ ማምራታቸውን አሳውቋል።
በመሆኑም ታዳጊዎቹ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድንን የወከሉ አለመሆኑን እየገለፅን በአንዳንድ አካላት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን አባላት እንደሆኑ እየተገለጸበት ያለው መንገድ ትክክል አለመሆኑን እናሳውቃለን ብሏል ፌደሬሽንኑ።
ፖሊስ የጠፉት ታዳጊዎች ዕድሜያቸው ከ14 እስከ 17 ዓመት የሆኑ ወጣቶች ሲሆኑ፣ ከእነሱ ጋር አንድ ወይም ከዚያ በላይ የቡድን መሪዎች አብረው ጠፍተዋል ብሏል። ይህ የታወቀው በውድድሩ የመጨረሻ ቀን ሲሆን ያረፉበት ትምህርት ቤት አስተዳዳሪ አባላቱ ያለ ምንም ማስታወቂያ ለቀው መሄዳቸውን ካረጋገጠ በኋላ ለፖሊስ ማሳወቁም ተዘግቧል።
Seledadotio
Seledadotio
ወደ ስዊድን ያቀኑ ዕድሜያቸው ከ 14 እስከ 17 የሚገመት 20 ታዳጊ የእግርኳስ ተጫዋቾች ከ መሪያቸው ጋር መጥፋታቸውን ስዊድን ሄራልድ ዘግቧል።
"ጎቲያካፕ" ለተሰኘ የእግር ኳስ ውድድር ከኢትዮጵያ የሔዱት ታዳጊዎች ካረፉበት ትምሕርት ቤት ሳያሳውቁ በመውጣት መሰወራቸውን የስዊድን ፖሊስ አስታውቋል።እግር ኳስ ተጫዋቾቹ ወደ ኢትዮጵያ እንዳልተመለሱ ያረጋገጠው ፖሊስ፤ በራሳቸው ፍላጎት ጠፍተው ሊሆን እንደሚችል አመላክቷል።
በጉዳዩ ዙርያ ምላሽ የሰጠው ፌደሬሽኑ የቡድኑ አባላት መጥፋት እንዳሳዘነው እና ታዳጊዎቹ በመሰል ውድድሮች ላይ በራሳቸው ጥረት በሚያገኙት እድል ወደ ውድድሩ ማምራታቸውን አሳውቋል።
በመሆኑም ታዳጊዎቹ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድንን የወከሉ አለመሆኑን እየገለፅን በአንዳንድ አካላት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን አባላት እንደሆኑ እየተገለጸበት ያለው መንገድ ትክክል አለመሆኑን እናሳውቃለን ብሏል ፌደሬሽንኑ።
ፖሊስ የጠፉት ታዳጊዎች ዕድሜያቸው ከ14 እስከ 17 ዓመት የሆኑ ወጣቶች ሲሆኑ፣ ከእነሱ ጋር አንድ ወይም ከዚያ በላይ የቡድን መሪዎች አብረው ጠፍተዋል ብሏል። ይህ የታወቀው በውድድሩ የመጨረሻ ቀን ሲሆን ያረፉበት ትምህርት ቤት አስተዳዳሪ አባላቱ ያለ ምንም ማስታወቂያ ለቀው መሄዳቸውን ካረጋገጠ በኋላ ለፖሊስ ማሳወቁም ተዘግቧል።
Seledadotio
Seledadotio
7 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) በስዊድን ጎተንበርግ ከተማ እየተካሄደ በሚገኘው የ'ጎቲያ ካፕ' የዓለም የወጣቶች እግር ኳስ ውድድር ላይ ለመሳተፍ ካቀኑት የኢትዮጵያ ቡድኖች መካከል፣ 20 የሚሆኑ የአንድ ቡድን ተጫዋቾች እና አጃቢ አዋቂዎች የውድድሩ ማጠቃለያ ዕለት ባልታሰበ ሁኔታ መሰወራቸው ተገልጿል። ይህ ክስተት በስፖርቱ ሽፋን በራሳቸው ፍቃድ የተፈጸመ ህገ-ወጥ ስደት (illegal migration) ሊሆን እንደሚችል የስዊድን ፖሊስ አስታውቋል።
ከ77 ሀገራት የተውጣጡ ቡድኖች በተሳተፉበት በዚህ ውድድር ኢትዮጵያ በአራት ቡድኖች ተወክላ ነበር። ሆኖም የፍጻሜው ውድድር በሚካሄድበት ዕለት የተጫዋቾቹ ማረፊያ የነበረው ትምህርት ቤት አስተናጋጆች፣ አባላቱ እቃቸውን ጠቅልለው መጥፋታቸውን ደርሰውበታል። የጎቲያ ካፕ የፕሬስ ቃል አቀባይ ፍሬድሪክ ቤክማን፣ አዘጋጁ ኮሚቴ ከቡድኑ ጋር ጥሩ ግንኙነት ስለነበረው ድርጊቱ እንዳስገረማቸው ገልጸው፣ ለጥንቃቄ ሲባል ለፖሊስ ሪፖርት ማድረጋቸውን ተናግረዋል። ውድድሩ ከተጠናቀቀ አስር ቀናት ቢያልፉም፣ የቡድኑ አባላት እስካሁን ወደ ኢትዮጵያ አልተመለሱም።
አዘጋጆቹ ከቡድኑ አስተባባሪ በደረሳቸው የኢሜል መልእክት "የተፈጠረው የመግባባት ችግር ነው" የሚል ማስተባበያ ቢሰጥም፣ ተጫዋቾቹ የት እንዳሉ ግን ምንም ዓይነት ፍንጭ አልተሰጠም። የስዊድን ፖሊስ የጠፉ ሰዎችን የመፈለግ ክፍል ኃላፊ ኤሊኖር ሃልዲን እንደገለጹት፣ ከዚህ በፊት በውድድሩ ታሪክ ጥቂት ሰዎች የመጥፋት አጋጣሚ ቢኖርም፣ በአንድ ጊዜ 20 ሰዎች ሲሰወሩ ግን ይህ የመጀመሪያው ነው።
ፖሊስ ከስደተኞች ኤጀንሲ እና ከድንበር ተቆጣጣሪዎች ጋር በመተባበር ፍለጋውን የቀጠለ ሲሆን፣ ድርጊቱ በሰው አዘዋዋሪዎች የተፈጸመ ሳይሆን አባላቱ አስቀድመው ያቀዱት ስደት መሆኑን መረጃዎች ያመለክታሉ።
ይህ ክስተት ዓለም አቀፍ ስፖርታዊ መድረኮች ላልተገባ የስደት ዓላማ መጠቀሚያ እየሆኑ መምጣታቸውን የሚያሳይ አሳሳቢ አጋጣሚ ሆኗል። ታዳጊ አትሌቶች እና አጃቢዎቻቸው ሀገራቸውን ወክለው በሄዱበት የውድድር መድረክ ላይ መሰወራቸው፣ በሀገራት መካከል ያለውን እምነት ከመፈተኑም በላይ፤ በቀጣይ ሌሎች ወጣት ኢትዮጵያውያን ስፖርተኞች ዓለም አቀፍ የውድድር ዕድሎችን እንዳያገኙ እና የቪዛ ክልከላ እንዲያጋጥማቸው ሊያደርግ የሚችል አደገኛ አዝማሚያ መሆኑ የጉዳዩን አሳሳቢነት ያጎላዋል።
የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ባወጣው መግለጫ፤ "ዓመታዊው የጎቲያ ካፕ ውድድር ላይ ለመካፈል ወደ ስዊድን ያመሩ ታዳጊዎች እና የቡድን አባላት በስዊድን መጥፋታቸውን አስመልክቶ የተለያዩ መረጃዎች እየወጡ ይገኛሉ። በጉዳዩ ዙርያ ምላሽ ወይም ማብራርያ እንድንሰጥ ወደ ኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ጥያቄዎች እየቀረቡ ሲሆን ፌዴሬሽናችን የቡድኑ አባላት መጥፋት ያሳዘነው መሆኑን እየገለጸ ታዳጊ ቡድኖች በመሰል ውድድሮች ላይ በራሳቸው ጥረት በሚያገኙት እድል ወደ ውድድሩ የሚያመሩ እንጂ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድንን የወከሉ አለመሆኑን እየገለፅን በአንዳድ አካላት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን አባላት እንደሆኑ እየተገለጸበት ያለው መንገድ ትክክል አለመሆኑን እናሳውቃለን። " ብሏል።
ከ77 ሀገራት የተውጣጡ ቡድኖች በተሳተፉበት በዚህ ውድድር ኢትዮጵያ በአራት ቡድኖች ተወክላ ነበር። ሆኖም የፍጻሜው ውድድር በሚካሄድበት ዕለት የተጫዋቾቹ ማረፊያ የነበረው ትምህርት ቤት አስተናጋጆች፣ አባላቱ እቃቸውን ጠቅልለው መጥፋታቸውን ደርሰውበታል። የጎቲያ ካፕ የፕሬስ ቃል አቀባይ ፍሬድሪክ ቤክማን፣ አዘጋጁ ኮሚቴ ከቡድኑ ጋር ጥሩ ግንኙነት ስለነበረው ድርጊቱ እንዳስገረማቸው ገልጸው፣ ለጥንቃቄ ሲባል ለፖሊስ ሪፖርት ማድረጋቸውን ተናግረዋል። ውድድሩ ከተጠናቀቀ አስር ቀናት ቢያልፉም፣ የቡድኑ አባላት እስካሁን ወደ ኢትዮጵያ አልተመለሱም።
አዘጋጆቹ ከቡድኑ አስተባባሪ በደረሳቸው የኢሜል መልእክት "የተፈጠረው የመግባባት ችግር ነው" የሚል ማስተባበያ ቢሰጥም፣ ተጫዋቾቹ የት እንዳሉ ግን ምንም ዓይነት ፍንጭ አልተሰጠም። የስዊድን ፖሊስ የጠፉ ሰዎችን የመፈለግ ክፍል ኃላፊ ኤሊኖር ሃልዲን እንደገለጹት፣ ከዚህ በፊት በውድድሩ ታሪክ ጥቂት ሰዎች የመጥፋት አጋጣሚ ቢኖርም፣ በአንድ ጊዜ 20 ሰዎች ሲሰወሩ ግን ይህ የመጀመሪያው ነው።
ፖሊስ ከስደተኞች ኤጀንሲ እና ከድንበር ተቆጣጣሪዎች ጋር በመተባበር ፍለጋውን የቀጠለ ሲሆን፣ ድርጊቱ በሰው አዘዋዋሪዎች የተፈጸመ ሳይሆን አባላቱ አስቀድመው ያቀዱት ስደት መሆኑን መረጃዎች ያመለክታሉ።
ይህ ክስተት ዓለም አቀፍ ስፖርታዊ መድረኮች ላልተገባ የስደት ዓላማ መጠቀሚያ እየሆኑ መምጣታቸውን የሚያሳይ አሳሳቢ አጋጣሚ ሆኗል። ታዳጊ አትሌቶች እና አጃቢዎቻቸው ሀገራቸውን ወክለው በሄዱበት የውድድር መድረክ ላይ መሰወራቸው፣ በሀገራት መካከል ያለውን እምነት ከመፈተኑም በላይ፤ በቀጣይ ሌሎች ወጣት ኢትዮጵያውያን ስፖርተኞች ዓለም አቀፍ የውድድር ዕድሎችን እንዳያገኙ እና የቪዛ ክልከላ እንዲያጋጥማቸው ሊያደርግ የሚችል አደገኛ አዝማሚያ መሆኑ የጉዳዩን አሳሳቢነት ያጎላዋል።
የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ባወጣው መግለጫ፤ "ዓመታዊው የጎቲያ ካፕ ውድድር ላይ ለመካፈል ወደ ስዊድን ያመሩ ታዳጊዎች እና የቡድን አባላት በስዊድን መጥፋታቸውን አስመልክቶ የተለያዩ መረጃዎች እየወጡ ይገኛሉ። በጉዳዩ ዙርያ ምላሽ ወይም ማብራርያ እንድንሰጥ ወደ ኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ጥያቄዎች እየቀረቡ ሲሆን ፌዴሬሽናችን የቡድኑ አባላት መጥፋት ያሳዘነው መሆኑን እየገለጸ ታዳጊ ቡድኖች በመሰል ውድድሮች ላይ በራሳቸው ጥረት በሚያገኙት እድል ወደ ውድድሩ የሚያመሩ እንጂ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድንን የወከሉ አለመሆኑን እየገለፅን በአንዳድ አካላት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን አባላት እንደሆኑ እየተገለጸበት ያለው መንገድ ትክክል አለመሆኑን እናሳውቃለን። " ብሏል።
Sponsored by
Surafel
7 days ago
የ16 ዓመቱ ታዳጊ የ10 ዓመቱን ህጻን አዳነ፤
* በትራምፕ ሊሸለም ነው!
#ethiopia | በአሜሪካ ካሊፎርኒያ ግዛት በሚገኘው የሴንታ ክሩዝ ሲብራይት (Seabright) የባህር ዳርቻ የ16 ዓመቱ ታዳጊ ላይፍጋርድ ራይደር ዊሊያምስ በኃይለኛ ማዕበል ተወስዶ ለሞት የተጋለጠን የ10 ዓመት ህጻን በጀግንነት በማዳኑ በመላው አሜሪካ ትልቅ አድናቆት እያገኘ ነው።
በምስክሮች በተቀረጸው ቪዲዮ መሠረት፣ ህጻኑ በድንገት በተነሳ ኃይለኛ ማዕበል ወደ ባህሩ ከተወሰደ በኋላ ራይደር ሳይዘገይ ወደ ውሃው ዘልቆ በመግባት ህጻኑን አጥብቆ ይዞ ከተደጋጋሚ ከባድ ማዕበሎች ጋር በመታገል እስከ ዳርቻ ድረስ ማድረስ ችሏል። በኋላም ሌላ ላይፍጋርድ በመድረስ ህጻኑ በደህና ወደ ዳርቻ ተወስዶ በሕክምና ከታየ በኋላ ለወላጆቹ ተሰጥቷል።
የማዳኑ ቪዲዮ በማህበራዊ ሚዲያ በስፋት ከተሰራጨ በኋላ ሚሊዮኖች ተመልካቾች ታዳጊውን "እውነተኛ ጀግና" በማለት ሲያወድሱት ታይቷል።
አባቱም ልጁ ከልጅነቱ ጀምሮ በውሃ ስፖርቶችና በላይፍጋርድ ስልጠና የተዘጋጀ መሆኑን ገልጾ፣ "ልጁን ፈጽሞ አልለቀቀውም" ብሏል።
የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕም በማህበራዊ ሚዲያ ባስተላለፉት መልእክት፣ ራይደርንና ቤተሰቡን እንዲሁም ያዳነውን ህጻን ወደ ነጩ ቤት በመጋበዝ ለታዳጊው "High Civilian Honor" የተባለውን ከፍተኛ የሲቪል ክብር ሽልማት እንደሚሰጡት አስታውቀዋል።
ራይደር ዊሊያምስ በበኩሉ፣ ይህ በቪዲዮ የተቀረጸው ማዳን ብቻ ሳይሆን በዚያው ቀን ከስራ በኋላ ሌሎች ሁለት ሰዎችንም ከአደገኛ ማዕበል ማዳኑን ገልጿል።
ሔኖክ ወ/ ገብርኤል
#ethiopia #getutemesgen #getunews #america #lifeguard #ryderwilliams
* በትራምፕ ሊሸለም ነው!
#ethiopia | በአሜሪካ ካሊፎርኒያ ግዛት በሚገኘው የሴንታ ክሩዝ ሲብራይት (Seabright) የባህር ዳርቻ የ16 ዓመቱ ታዳጊ ላይፍጋርድ ራይደር ዊሊያምስ በኃይለኛ ማዕበል ተወስዶ ለሞት የተጋለጠን የ10 ዓመት ህጻን በጀግንነት በማዳኑ በመላው አሜሪካ ትልቅ አድናቆት እያገኘ ነው።
በምስክሮች በተቀረጸው ቪዲዮ መሠረት፣ ህጻኑ በድንገት በተነሳ ኃይለኛ ማዕበል ወደ ባህሩ ከተወሰደ በኋላ ራይደር ሳይዘገይ ወደ ውሃው ዘልቆ በመግባት ህጻኑን አጥብቆ ይዞ ከተደጋጋሚ ከባድ ማዕበሎች ጋር በመታገል እስከ ዳርቻ ድረስ ማድረስ ችሏል። በኋላም ሌላ ላይፍጋርድ በመድረስ ህጻኑ በደህና ወደ ዳርቻ ተወስዶ በሕክምና ከታየ በኋላ ለወላጆቹ ተሰጥቷል።
የማዳኑ ቪዲዮ በማህበራዊ ሚዲያ በስፋት ከተሰራጨ በኋላ ሚሊዮኖች ተመልካቾች ታዳጊውን "እውነተኛ ጀግና" በማለት ሲያወድሱት ታይቷል።
አባቱም ልጁ ከልጅነቱ ጀምሮ በውሃ ስፖርቶችና በላይፍጋርድ ስልጠና የተዘጋጀ መሆኑን ገልጾ፣ "ልጁን ፈጽሞ አልለቀቀውም" ብሏል።
የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕም በማህበራዊ ሚዲያ ባስተላለፉት መልእክት፣ ራይደርንና ቤተሰቡን እንዲሁም ያዳነውን ህጻን ወደ ነጩ ቤት በመጋበዝ ለታዳጊው "High Civilian Honor" የተባለውን ከፍተኛ የሲቪል ክብር ሽልማት እንደሚሰጡት አስታውቀዋል።
ራይደር ዊሊያምስ በበኩሉ፣ ይህ በቪዲዮ የተቀረጸው ማዳን ብቻ ሳይሆን በዚያው ቀን ከስራ በኋላ ሌሎች ሁለት ሰዎችንም ከአደገኛ ማዕበል ማዳኑን ገልጿል።
ሔኖክ ወ/ ገብርኤል
#ethiopia #getutemesgen #getunews #america #lifeguard #ryderwilliams
7 days ago
በጎቲያ ካፕ የተሳተፉ 20 የሚጠጉ ኢትዮጵያውያን ታዳጊ ተጫዋቾችና የቡድን አመራሮች በስዊድን መሰወራቸው ተረጋገጠ
#ethiopia | በስዊድን ጎተንበርግ ከተማ በተካሄደው የ2026 የ«ጎቲያ ካፕ» ዓለም አቀፍ የታዳጊዎች እግር ኳስ ውድድር ላይ የተሳተፉ 20 የሚጠጉ ኢትዮጵያውያን ታዳጊ ተጫዋቾችና ቢያንስ አንድ የቡድን አመራር አባል ከውድድሩ በኋላ መሰወራቸውን የስዊድን ፖሊስ አረጋግጧል።
በስዊድን ፖሊስ መረጃ መሠረት፣ ቡድኑ ያረፈበትን ትምህርት ቤት ለቆ ያለማሳወቅ እንደወጣ ከታወቀ በኋላ ለፖሊስ ሪፖርት ተደርጓል። ፖሊስ እስካሁን የወንጀል፣ የሰው ዝውውር ወይም የግዳጅ ማስጠፋት ምልክት እንዳልተገኘ ገልጾ፣ ድርጊቱ በራሳቸው ፈቃድ የተፈጸመ እንደሚመስል አስታውቋል።
የጎቲያ ካፕ አዘጋጆች በበኩላቸው ከቡድኑ አንድ አመራር ጋር ግንኙነት እንዳደረጉ ገልጸው፣ ተጫዋቾቹ ከቤተሰቦቻቸው ጋር መገናኘታቸውንና በደህና መሆናቸውን ቢናገርም፣ አሁን የሚገኙበት ቦታ እንደማይታወቅ ገልጸዋል።
በኢትዮጵያ በኩል የእግር ኳስ ፌዴሬሽኑ የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ኃላፊ አቶ አብርሃም ገብረማሪያም፣ የተሰራጨው መረጃ እውነት መሆኑን አረጋግጠው፣ ወደ ስዊድን የሄደው ቡድን የኢትዮጵያን ብሔራዊ ቡድን ወክሎ የተላከ ሳይሆን በግል አደረጃጀት የተሰባሰበ ቡድን መሆኑን ገልጸዋል። በተጨማሪም ፌዴሬሽኑ በጉዳዩ ላይ ዝርዝር መግለጫ እንደሚያወጣ አስታውቋል።
«ጎቲያ ካፕ» በዓለም ላይ ትልቁ የታዳጊዎች የእግር ኳስ ውድድር ሲሆን፣ በ2026 ውድድሩ ከ78 አገራት የመጡ ከ45,000 በላይ ተጫዋቾችና አሰልጣኞች ተሳትፈዋል።
#ethiopia #gothiacup #sweden #sportsnews #getutemesgen #getunews
#ethiopia | በስዊድን ጎተንበርግ ከተማ በተካሄደው የ2026 የ«ጎቲያ ካፕ» ዓለም አቀፍ የታዳጊዎች እግር ኳስ ውድድር ላይ የተሳተፉ 20 የሚጠጉ ኢትዮጵያውያን ታዳጊ ተጫዋቾችና ቢያንስ አንድ የቡድን አመራር አባል ከውድድሩ በኋላ መሰወራቸውን የስዊድን ፖሊስ አረጋግጧል።
በስዊድን ፖሊስ መረጃ መሠረት፣ ቡድኑ ያረፈበትን ትምህርት ቤት ለቆ ያለማሳወቅ እንደወጣ ከታወቀ በኋላ ለፖሊስ ሪፖርት ተደርጓል። ፖሊስ እስካሁን የወንጀል፣ የሰው ዝውውር ወይም የግዳጅ ማስጠፋት ምልክት እንዳልተገኘ ገልጾ፣ ድርጊቱ በራሳቸው ፈቃድ የተፈጸመ እንደሚመስል አስታውቋል።
የጎቲያ ካፕ አዘጋጆች በበኩላቸው ከቡድኑ አንድ አመራር ጋር ግንኙነት እንዳደረጉ ገልጸው፣ ተጫዋቾቹ ከቤተሰቦቻቸው ጋር መገናኘታቸውንና በደህና መሆናቸውን ቢናገርም፣ አሁን የሚገኙበት ቦታ እንደማይታወቅ ገልጸዋል።
በኢትዮጵያ በኩል የእግር ኳስ ፌዴሬሽኑ የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ኃላፊ አቶ አብርሃም ገብረማሪያም፣ የተሰራጨው መረጃ እውነት መሆኑን አረጋግጠው፣ ወደ ስዊድን የሄደው ቡድን የኢትዮጵያን ብሔራዊ ቡድን ወክሎ የተላከ ሳይሆን በግል አደረጃጀት የተሰባሰበ ቡድን መሆኑን ገልጸዋል። በተጨማሪም ፌዴሬሽኑ በጉዳዩ ላይ ዝርዝር መግለጫ እንደሚያወጣ አስታውቋል።
«ጎቲያ ካፕ» በዓለም ላይ ትልቁ የታዳጊዎች የእግር ኳስ ውድድር ሲሆን፣ በ2026 ውድድሩ ከ78 አገራት የመጡ ከ45,000 በላይ ተጫዋቾችና አሰልጣኞች ተሳትፈዋል።
#ethiopia #gothiacup #sweden #sportsnews #getutemesgen #getunews
8 days ago
“በስዊድን የጠፉት ታዳጊዎች ብሔራዊ ቡድንን አይወክሉም”
— የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን
#ethiopia | በዓመታዊው የጎቲያ ካፕ ውድድር ላይ ለመካፈል ወደ ስዊድን ያመሩ ታዳጊዎች እና የቡድን አባላት በዚያው መጥፋታቸውን የሚያመላክቱ መረጃዎች መውጣታቸውን ተከትሎ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ማብራሪያ ሰጥቷል።
ፌዴሬሽኑ በቡድኑ አባላት መጥፋት እንደሰማ የገለጸ ሲሆን በተለያዩ አካላት ታዳጊዎቹ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ተወካዮች እንደሆኑ ተደርጎ የሚሰራጨው ዘገባም ሙሉ በሙሉ ትክክል እንዳልሆነ አስታውቋል።
አክሎም መሰል ታዳጊ ቡድኖች ወደ እንዲህ ባሉ ዓለም አቀፍ ውድድሮች የሚያመሩት በራሳቸው ጥረት በሚያገኙት እድል እንጂ አገራቸውን ወክለው በፌዴሬሽኑ አደራጅነት እንዳልሆነ በመግለጽ ጉዳዩን አብራርቷል።
በያፌት ገ/ህይወት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
— የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን
#ethiopia | በዓመታዊው የጎቲያ ካፕ ውድድር ላይ ለመካፈል ወደ ስዊድን ያመሩ ታዳጊዎች እና የቡድን አባላት በዚያው መጥፋታቸውን የሚያመላክቱ መረጃዎች መውጣታቸውን ተከትሎ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ማብራሪያ ሰጥቷል።
ፌዴሬሽኑ በቡድኑ አባላት መጥፋት እንደሰማ የገለጸ ሲሆን በተለያዩ አካላት ታዳጊዎቹ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ተወካዮች እንደሆኑ ተደርጎ የሚሰራጨው ዘገባም ሙሉ በሙሉ ትክክል እንዳልሆነ አስታውቋል።
አክሎም መሰል ታዳጊ ቡድኖች ወደ እንዲህ ባሉ ዓለም አቀፍ ውድድሮች የሚያመሩት በራሳቸው ጥረት በሚያገኙት እድል እንጂ አገራቸውን ወክለው በፌዴሬሽኑ አደራጅነት እንዳልሆነ በመግለጽ ጉዳዩን አብራርቷል።
በያፌት ገ/ህይወት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
8 days ago
በስዊድን የጎቲያ ካፕ ላይ የተሳተፉ 20 ያህል ኢትዮጵያውያን የቡድን አባላት መጥፋታቸው ተገለጸ
#fastmereja | በስዊድን ጎተንበርግ ከተማ በተካሄደው የጎቲያ ታዳጊዎች ውድድር (Gothia Cup) ላይ ለመሳተፍ የተጓዙ 20 ያህል ኢትዮጵያውያን ተጫዋቾች እና የቡድን መሪዎች ደብዛቸው መጥፋቱን የስዊድን ፖሊስ እና የውድድሩ አዘጋጆች አስታወቁ።
በየዓመቱ በስዊድን በሚካሄደው ዓለም አቀፍ የታዳጊዎች እግር ኳስ ውድድር ላይ ከተሳተፉ አራት የኢትዮጵያ ቡድኖች መካከል የአንዱ ቡድን አባላት የሆኑት እነዚህ 20 ያህል ግለሰቦች፣ ውድድሩ በተጠናቀቀበት የመጨረሻ ቀን ያረፉበት ትምህርት ቤት ሳይሰናበቱ መውጣታቸው ተሰምቷል። የቡድኑ አባላት እድሜያቸው ከ14 እስከ 17 ዓመት የሆኑ ታዳጊ ተጫዋቾችን እና ከአሰልጣኞች ወይም መሪዎች መካከል የተወሰኑትን ያካተተ መሆኑ ተመልክቷል።
የውድድሩ አዘጋጆች የቡድኑን መጥፋት እንደተረዱ ለአካባቢው ፖሊስ ጥቆማ ያቀረቡ ሲሆን፣ ቡድኑ ወደ ዋና ከተማዋ ስቶክሆልም አቅጣጫ ተጓዥ መሆናቸውን ጠቁመዋል። የስዊድን ፖሊስ ባደረገው ማጣራት እነዚህ ግለሰቦች ወደ ኢትዮጵያ እንዳልተመለሱ ያረጋገጠ ሲሆን፣ ክስተቱ በራሳቸው ፍላጎት የተደረገ መሰወር ወይም ህገ-ወጥ የፍልሰት እንቅስቃሴ እንደሆነ መገመቱን ገልጻል።
የስዊድን የምዕራብ ክልል ፖሊስ የጠፉ ሰዎች ክፍል ተወካይ ኤሊኖር ሃልዲን እንደገለጹት፣ በጉዳዩ ላይ የሰዎች ዝውውር ወይም የወንጀል ድርጊት መኖሩን የሚያሳይ ፍንጭ እስካሁን አልተገኘም። ሆኖም የስዊድን ፖሊስ ከአገሪቱ የኢሚግሬሽን መሥሪያ ቤት፣ ከድንበር ጠባቂዎች እና ከአለም አቀፍ አጋሮች ጋር በመተባበር የቡድኑን አባላት የመፈለግ ሥራ አጠናክሮ መቀጠሉን አስታውቋል።
#fastmereja | በስዊድን ጎተንበርግ ከተማ በተካሄደው የጎቲያ ታዳጊዎች ውድድር (Gothia Cup) ላይ ለመሳተፍ የተጓዙ 20 ያህል ኢትዮጵያውያን ተጫዋቾች እና የቡድን መሪዎች ደብዛቸው መጥፋቱን የስዊድን ፖሊስ እና የውድድሩ አዘጋጆች አስታወቁ።
በየዓመቱ በስዊድን በሚካሄደው ዓለም አቀፍ የታዳጊዎች እግር ኳስ ውድድር ላይ ከተሳተፉ አራት የኢትዮጵያ ቡድኖች መካከል የአንዱ ቡድን አባላት የሆኑት እነዚህ 20 ያህል ግለሰቦች፣ ውድድሩ በተጠናቀቀበት የመጨረሻ ቀን ያረፉበት ትምህርት ቤት ሳይሰናበቱ መውጣታቸው ተሰምቷል። የቡድኑ አባላት እድሜያቸው ከ14 እስከ 17 ዓመት የሆኑ ታዳጊ ተጫዋቾችን እና ከአሰልጣኞች ወይም መሪዎች መካከል የተወሰኑትን ያካተተ መሆኑ ተመልክቷል።
የውድድሩ አዘጋጆች የቡድኑን መጥፋት እንደተረዱ ለአካባቢው ፖሊስ ጥቆማ ያቀረቡ ሲሆን፣ ቡድኑ ወደ ዋና ከተማዋ ስቶክሆልም አቅጣጫ ተጓዥ መሆናቸውን ጠቁመዋል። የስዊድን ፖሊስ ባደረገው ማጣራት እነዚህ ግለሰቦች ወደ ኢትዮጵያ እንዳልተመለሱ ያረጋገጠ ሲሆን፣ ክስተቱ በራሳቸው ፍላጎት የተደረገ መሰወር ወይም ህገ-ወጥ የፍልሰት እንቅስቃሴ እንደሆነ መገመቱን ገልጻል።
የስዊድን የምዕራብ ክልል ፖሊስ የጠፉ ሰዎች ክፍል ተወካይ ኤሊኖር ሃልዲን እንደገለጹት፣ በጉዳዩ ላይ የሰዎች ዝውውር ወይም የወንጀል ድርጊት መኖሩን የሚያሳይ ፍንጭ እስካሁን አልተገኘም። ሆኖም የስዊድን ፖሊስ ከአገሪቱ የኢሚግሬሽን መሥሪያ ቤት፣ ከድንበር ጠባቂዎች እና ከአለም አቀፍ አጋሮች ጋር በመተባበር የቡድኑን አባላት የመፈለግ ሥራ አጠናክሮ መቀጠሉን አስታውቋል።
9 days ago
በሳዑዲ ዓረቢያ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የነበሩ ከ1ሺህ በላይ ኢትዮጵያውያን ወደ ሀገራቸው ተመልሰዋል ተባለ፡፡
በሳምንት ውስጥ በተደረገ 8 ዙር በረራ የተመለሱት 1ሺህ 604 ወንዶችና 1መቶ92 ሴቶች አመት እንዲሁም 38 ጨቅላ ህፃናት ሲሆኑ፤ ከተመላሾች መካከል 53 እድሜያቸው ከአስራ ስምንት አመት በታች የሆኑ ታዳጊዎች ይገኙበታል ተብሏል።
የሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ለተመላሽ ዜጎች በአየር ማረፊያና በማቆያ ማዕከላት ተገቢውን ድጋፍ እና እንክብካቤ የማድረግ እና ከቤተሰብ ጋር የማቀላቀል ስራ ከሚመለከታቸው ባለድርሻና አጋር አካላት ጋር በመተባበር በትኩረት እየሰራ እንደሚገኝ አስታዉቋል፡፡
በተጨማሪም መደበኛ ባልሆነ ፍልሰት ወደ ተለያዩ ሀገራት ሄደው የሚመለሱ የፍልሰት ተጎጂዎችን ለመደገፍና መልሶ ለማቋቋም የሚያስችሉ ተግባራትን በትብብር እያከናወነ መሆኑን ገልጿል፡፡
ወደፊትም በህገወጥ የሰዎች ዝውውር አስከፊነት ዙሪያ ህብረተሰቡን ለማስገንዘብ፣ መደበኛ ያልሆነ ፍልሰትን ለመከላከልና ደህንነቱ የተጠበቀ ፍልሰትን ለማበረታታት ሚኒስቴሩ የጀመራቸውን ስራዎች አጠናክሮ የሚቀጥል ይሆናል ተብሏል።
በአጠቃላይ 1ሺህ 8መቶ 34 ዜጎች ወደ አገር ዉስጥ ተመልሰዋል መባሉን የሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል፡፡
Seledadotio
Seledadotio
በሳምንት ውስጥ በተደረገ 8 ዙር በረራ የተመለሱት 1ሺህ 604 ወንዶችና 1መቶ92 ሴቶች አመት እንዲሁም 38 ጨቅላ ህፃናት ሲሆኑ፤ ከተመላሾች መካከል 53 እድሜያቸው ከአስራ ስምንት አመት በታች የሆኑ ታዳጊዎች ይገኙበታል ተብሏል።
የሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ለተመላሽ ዜጎች በአየር ማረፊያና በማቆያ ማዕከላት ተገቢውን ድጋፍ እና እንክብካቤ የማድረግ እና ከቤተሰብ ጋር የማቀላቀል ስራ ከሚመለከታቸው ባለድርሻና አጋር አካላት ጋር በመተባበር በትኩረት እየሰራ እንደሚገኝ አስታዉቋል፡፡
በተጨማሪም መደበኛ ባልሆነ ፍልሰት ወደ ተለያዩ ሀገራት ሄደው የሚመለሱ የፍልሰት ተጎጂዎችን ለመደገፍና መልሶ ለማቋቋም የሚያስችሉ ተግባራትን በትብብር እያከናወነ መሆኑን ገልጿል፡፡
ወደፊትም በህገወጥ የሰዎች ዝውውር አስከፊነት ዙሪያ ህብረተሰቡን ለማስገንዘብ፣ መደበኛ ያልሆነ ፍልሰትን ለመከላከልና ደህንነቱ የተጠበቀ ፍልሰትን ለማበረታታት ሚኒስቴሩ የጀመራቸውን ስራዎች አጠናክሮ የሚቀጥል ይሆናል ተብሏል።
በአጠቃላይ 1ሺህ 8መቶ 34 ዜጎች ወደ አገር ዉስጥ ተመልሰዋል መባሉን የሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል፡፡
Seledadotio
Seledadotio
Sponsored by
Surafel
12 days ago
ለአፍሪካውያን ታዳጊዎች የህልም ምሳሌ የሆኑት ጥቋቁር ወርቆች መድመቃቸውን ቀጥለዋል።
*ከጎዳና ህይወት እስከ አለም አቀፍ መድረክ
*አስከፊ ከሆነ የጎዳና ህይወት ተነስተው ከዝነኛዋ ሻኪራ ጋር እስከ መጣመር የደረሱት ጥቋቁር የአፍሪካ ወርቆች
#ethiopia | በምስራቅ አፍሪካ የጥበብ ዓለም ውስጥ የብዙዎችን ቀልብ የሳቡት የኡጋንዳው የዳንስ ቡድን ጌቶ ኪድስ የችሎታ እና የጽናት ተምሳሌት በመሆን ዓለምን እያስደነቁ ይገኛሉ።
ቡድኑ የተመሰረተው በኡጋንዳዋ ካምፓላ ከተማ በሚገኘው የካታዌ (Katwe) ሰፈር ነው።
በዳውዳ ካቫማ አማካኝነት የተደራጁት እነዚህ ታዳጊዎች መነሻቸው ከምንም ነበር ማለት ይቻላል።
እነዚህ ህጻናት በተስፋ መቁረጥ ውስጥ የነበሩ ከድህነት ጋር በጎዳና ህይወት ላይ የነበሩ ናቸው።
ይህ ብልሁ ዳውዳ ካቫማ የተባለው ወጣት ታዳጊዎችን በመሰብሰብ በሙዚቃ እና በዳንስ ተስፋ እንዲሰንቁ ብሎም ስማቸውን አለም እንዲያውቀው አድርጓል።
የዳውዳ ካቫማ አላማ የነበረው መዝናኛን ብቻ ሳይሆን ችሎታን በመጠቀም የጎዳና ላይ ህይወት በአማራጭ መንገድ ሊቀየር እንደሚችል ለዓለም ማሳየት ነበር።
ቡድኑ መጀመሪያ ላይ ትኩረት ያደረገው ጎዳና ላይ በመጨፈር የነበረ ሲሆን የነበራቸው ጉልበት እና ተፈጥሯዊ የዳንስ ችሎታ በየማህበራዊ ሚዲያው በወጡ አጫጭር ቪዲዮዎች የዓለምን ትኩረት በቶሎ እንዲስቡ አድርጓቸዋል።
ጌቶ ኪድስ ከኡጋንዳ አልፈው ዓለም አቀፍ እውቅና ያገኙት በተለያዩ የዓለም የሙዚቃ ቪዲዮዎች ላይ በመሳተፍ ነው።
በተለይም በፈረንጆቹ 2017 ላይ ከፈረንሳዊው አርቲስት ፍሬንች ሞንታና (French Montana) ጋር በሰሩት "Unforgettable" የሙዚቃ ቪዲዮ አማካኝነት ስማቸው በዓለም አቀፍ ደረጃ በሰፊው ተሰማ።
ጌቶ ኪድስ በዓለም አቀፍ ደረጃ በታላላቅ የሙዚቃ ሽልማቶች ላይ ተጋባዥ ሆነዋል።
በዓለም አቀፍ የቴሌቪዥን ፕሮግራሞች ላይ በመቅረብ የኡጋንዳን እና የአፍሪካን ስም በከፍተኛ ደረጃ እያስጠሩም ይገኛሉ።
በቅርቡ በተጠናቀቀው የ2026 የዓለም ዋንጫ የፍጻሜ ጨዋታ ላይ ከዝነኛዋ ሻኪራ ጋር በመጣመር ባሳዩት ብቃት የስኬት ጉዟቸውን ከፍታ ላይ አድርሰውታል።
ዛሬ "ጌቶ ኪድስ" የዳንስ ቡድን ብቻ ሳይሆን የበርካታ አፍሪካውያን ታዳጊዎች የህልም ምሳሌ ሆነዋል።
ሔኖክ ወ/ገብርኤል
#ethiopia #getutemesgen #getunews #ugandaghettokids #dancingwithshakira #worldcupfinal
*ከጎዳና ህይወት እስከ አለም አቀፍ መድረክ
*አስከፊ ከሆነ የጎዳና ህይወት ተነስተው ከዝነኛዋ ሻኪራ ጋር እስከ መጣመር የደረሱት ጥቋቁር የአፍሪካ ወርቆች
#ethiopia | በምስራቅ አፍሪካ የጥበብ ዓለም ውስጥ የብዙዎችን ቀልብ የሳቡት የኡጋንዳው የዳንስ ቡድን ጌቶ ኪድስ የችሎታ እና የጽናት ተምሳሌት በመሆን ዓለምን እያስደነቁ ይገኛሉ።
ቡድኑ የተመሰረተው በኡጋንዳዋ ካምፓላ ከተማ በሚገኘው የካታዌ (Katwe) ሰፈር ነው።
በዳውዳ ካቫማ አማካኝነት የተደራጁት እነዚህ ታዳጊዎች መነሻቸው ከምንም ነበር ማለት ይቻላል።
እነዚህ ህጻናት በተስፋ መቁረጥ ውስጥ የነበሩ ከድህነት ጋር በጎዳና ህይወት ላይ የነበሩ ናቸው።
ይህ ብልሁ ዳውዳ ካቫማ የተባለው ወጣት ታዳጊዎችን በመሰብሰብ በሙዚቃ እና በዳንስ ተስፋ እንዲሰንቁ ብሎም ስማቸውን አለም እንዲያውቀው አድርጓል።
የዳውዳ ካቫማ አላማ የነበረው መዝናኛን ብቻ ሳይሆን ችሎታን በመጠቀም የጎዳና ላይ ህይወት በአማራጭ መንገድ ሊቀየር እንደሚችል ለዓለም ማሳየት ነበር።
ቡድኑ መጀመሪያ ላይ ትኩረት ያደረገው ጎዳና ላይ በመጨፈር የነበረ ሲሆን የነበራቸው ጉልበት እና ተፈጥሯዊ የዳንስ ችሎታ በየማህበራዊ ሚዲያው በወጡ አጫጭር ቪዲዮዎች የዓለምን ትኩረት በቶሎ እንዲስቡ አድርጓቸዋል።
ጌቶ ኪድስ ከኡጋንዳ አልፈው ዓለም አቀፍ እውቅና ያገኙት በተለያዩ የዓለም የሙዚቃ ቪዲዮዎች ላይ በመሳተፍ ነው።
በተለይም በፈረንጆቹ 2017 ላይ ከፈረንሳዊው አርቲስት ፍሬንች ሞንታና (French Montana) ጋር በሰሩት "Unforgettable" የሙዚቃ ቪዲዮ አማካኝነት ስማቸው በዓለም አቀፍ ደረጃ በሰፊው ተሰማ።
ጌቶ ኪድስ በዓለም አቀፍ ደረጃ በታላላቅ የሙዚቃ ሽልማቶች ላይ ተጋባዥ ሆነዋል።
በዓለም አቀፍ የቴሌቪዥን ፕሮግራሞች ላይ በመቅረብ የኡጋንዳን እና የአፍሪካን ስም በከፍተኛ ደረጃ እያስጠሩም ይገኛሉ።
በቅርቡ በተጠናቀቀው የ2026 የዓለም ዋንጫ የፍጻሜ ጨዋታ ላይ ከዝነኛዋ ሻኪራ ጋር በመጣመር ባሳዩት ብቃት የስኬት ጉዟቸውን ከፍታ ላይ አድርሰውታል።
ዛሬ "ጌቶ ኪድስ" የዳንስ ቡድን ብቻ ሳይሆን የበርካታ አፍሪካውያን ታዳጊዎች የህልም ምሳሌ ሆነዋል።
ሔኖክ ወ/ገብርኤል
#ethiopia #getutemesgen #getunews #ugandaghettokids #dancingwithshakira #worldcupfinal
13 days ago
ኤንድሪክ እንደ አንጀሊና ጆሊ
#ethiopia | የሪያል ማድሪዱ አጥቂ ኤንደሪክ የተባበሩት መንግስታት የህጻናት አድን ድርጅት (ዩኒሴፍ) የብራዚል አምባሳደር ሆኖ መሾሙን ተቋሙ አስታወቀ።
የ20 ዓመቱ እግር ኳስ ተጫዋች ኤንድሪክ የህጻናትን መብት ለማስከበር እና በሀገሪቱ የዩኒሴፍን እንቅስቃሴዎች ለመደገፍ በብራዚል የዩኒሴፍ አምባሳደር ሆኖ ተሹሟል።
የብራዚል ብሔራዊ ቡድን እና የሪያል ማድሪድ ተጫዋች የሆነው ኤንደሪክ ከዚህ በኋላ በሀገሪቱ የህጻናት እና ታዳጊዎች መብትን ለማስከበር ከሌሎች የዩኒሴፍ አምባሳደሮች ጋር በጋራ እንደሚሰራ ተገልጿል።
ኤንድሪክ ያለው ተጽዕኖ እና የሚያሳየው አርአያነት ለዚህ የኃላፊነት ሚና ትክክለኛ ተመራጭ እንዲሆን አድርጎታል።
ዩኒሴፍ ከ1954 ዓ.ም ጀምሮ በአለም ዙሪያ አምባሳደሮችን ሲሾም ቆይቷል።
እነዚህ አምባሳደሮች የሚመረጡት በስራቸው በሰፊው የሚታወቁ ተጽዕኖ ፈጣሪ እና የህጻናትንና የወጣቶችን ህይወት ለማሻሻል ከፍተኛ ቁርጠኝነት ያላቸው በመሆናቸው ነው።
በተለይም መልካም ምሳሌ መሆን የሚችሉ አርቲስቶች አትሌቶች እና ሌሎች ታዋቂ ግለሰቦች ለዚህ ቦታ በተለያዩ ጊዜያት ይሾማሉ።
ሔኖክ ወ/ገብርኤል
#ethiopia #getutemesgen #getunews #endricknamedunicef #ambassadorinbrazil #usaangelinajolie
#ethiopia | የሪያል ማድሪዱ አጥቂ ኤንደሪክ የተባበሩት መንግስታት የህጻናት አድን ድርጅት (ዩኒሴፍ) የብራዚል አምባሳደር ሆኖ መሾሙን ተቋሙ አስታወቀ።
የ20 ዓመቱ እግር ኳስ ተጫዋች ኤንድሪክ የህጻናትን መብት ለማስከበር እና በሀገሪቱ የዩኒሴፍን እንቅስቃሴዎች ለመደገፍ በብራዚል የዩኒሴፍ አምባሳደር ሆኖ ተሹሟል።
የብራዚል ብሔራዊ ቡድን እና የሪያል ማድሪድ ተጫዋች የሆነው ኤንደሪክ ከዚህ በኋላ በሀገሪቱ የህጻናት እና ታዳጊዎች መብትን ለማስከበር ከሌሎች የዩኒሴፍ አምባሳደሮች ጋር በጋራ እንደሚሰራ ተገልጿል።
ኤንድሪክ ያለው ተጽዕኖ እና የሚያሳየው አርአያነት ለዚህ የኃላፊነት ሚና ትክክለኛ ተመራጭ እንዲሆን አድርጎታል።
ዩኒሴፍ ከ1954 ዓ.ም ጀምሮ በአለም ዙሪያ አምባሳደሮችን ሲሾም ቆይቷል።
እነዚህ አምባሳደሮች የሚመረጡት በስራቸው በሰፊው የሚታወቁ ተጽዕኖ ፈጣሪ እና የህጻናትንና የወጣቶችን ህይወት ለማሻሻል ከፍተኛ ቁርጠኝነት ያላቸው በመሆናቸው ነው።
በተለይም መልካም ምሳሌ መሆን የሚችሉ አርቲስቶች አትሌቶች እና ሌሎች ታዋቂ ግለሰቦች ለዚህ ቦታ በተለያዩ ጊዜያት ይሾማሉ።
ሔኖክ ወ/ገብርኤል
#ethiopia #getutemesgen #getunews #endricknamedunicef #ambassadorinbrazil #usaangelinajolie
13 days ago
የክርስቶስ ዞሊስ የህይወትና የእግር ኳስ ጉዞ
ከተሰሎንቄ የጎዳና ኳስ እስከ ኤምሬትስ
ክርስቶስ ዞሊስ (Christos Tzolis) ጥር 30 ቀን 2002 ዓ.ም በግሪክ በመፅሃፍ ቅዱስ የምናውቃት ታሪካዊቷ ከተማ ተሰሎንቄ (Thessaloniki) ተወለደ። ወላጆቹ ከአልባንያ የመጡ የኦርቶዶክስ ግሪካውያን ዘሮች (Greek minority) ሲሆኑ በጽኑ የሃይማኖት ባህልና በኦርቶዶክስ ክርስትና እሴቶች ውስጥ አድጓል።
«ክርስቶስ» የሚለው መጠሪያ ስሙም በግሪክ ኦርቶዶክስ እምነት ባህል መሠረት ከፍተኛ መንፈሳዊ ትርጉም ያለው ሲሆን በግል ህይወቱ እና በስፖርታዊ እንቅስቃሴዎቹ ውስጥ የእምነቱ ተጽዕኖ በግልጽ ይንጸባረቃል።
ዞሊስ ገና በ4 ዓመቱ ዶክሳ ፔንታሎፎስ በተባለ የአካባቢው አካዳሚ እግር ኳስ መጫወት የጀመረ ሲሆን በ2010 ወደ ሀገሪቱ ታላቅ ክለብ PAOK Thessaloniki ታዳጊ ቡድን ተቀላቀለ።
በ18 ዓመቱ በዋናው ቡድን ውስጥ ድንቅ ብቃቱን ማሳየት ጀመረ። በሁለት የውድድር ዘመናት ውስጥ በበ57 ጨዋታዎች 17 ግቦችን በማስቆጠር የዓመቱ ኮከብ ወጣት ተጫዋች እና የካፕ ውድድሩ ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪ በመሆን ድቅድቅ አቅሙን አሳየ።
በ2021 ኖርዊች ሲቲ በ11 ሚሊዮን ዩሮ ገደማ ወደ ፕሪመር ሊግ ቢያስፈርመውም በቂ የጨዋታ ዕድል ባለማግኘቱ ፈታኝ ጊዜ አሳለፈ (በኖርዊች እና በውሰት በኔዘርላንዱ ቴቨንቴ በድምሩ 45 ጨዋታዎች 6 ግቦች ብቻ)።
ሆኖም በ2023–24 የውድድር ዘመን በውሰት ወደ ጀርመኑ ፎርቱና ዱሰልዶርፍ ማምራቱ የሙያ ህይወቱን ሙሉ በሙሉ ለወጠው፦
በ30 የሊግ ጨዋታዎች 22 ግቦችን በማስቆጠር የ2ኛው ቡንደስሊጋ ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪ (Top Scorer) በመሆን አጠናቀቀ።
በ2024 ወደ ቤልጅየሙ ክለብ ብሩጅ (Club Brugge) የተዛወረው ዞሊስ፣ በአውሮፓ መድረክ ትልቅ ስም መገንባት ቻለ፦
2024–2026 (Club Brugge)በ108 ጨዋታዎች 43 ግቦችን አስቆጥሯል።
በተለይም ባለፈው የውድድር ዘመን በሁሉም ውድድሮች 22 ግቦችን በማስቆጠር እና 29 ግቦችን አመቻችቶ በመስጠት (51 G/A) የቤልጅየም ሊግ የዓመቱ ኮከብ ተጫዋች (Player of the Season) ሽልማትን አሸንፏል።
በቻምፒየንስ ሊግም ቢሆን በዋና ዋና ቡድኖች ላይ ያስቆጠራቸው ግቦች የትልልቅ ክለቦችን ትኩረት ስበዋል።
በ2020 ገና በ18 ዓመቱ የብሔራዊ ቡድኑን ማልያ የለበሰ ሲሆን በታሪክ 7ኛው ትንሹ ተጫዋች ሆኖ ተመዝግቧል። እስካሁን ለግሪክ በ20+ ጨዋታዎች ተሰልፎ 5+ ግቦችን አስቆጥሯል።
በሚኬል አርቴታ ጥራት ያለው የግራ መስመር አጥቂ ፍለጋ መሠረትአርሰናል በ£34 ሚሊዮን ክፍያ አስፈርሞታል። በፈጣን ድሪብሊንግ፣ ከሳጥን ውጭ በሚመታቸው ጠንካራ ኳሶች እና በስብዕናው አርሰናልን በግራ መስመር ትልቅ ጥንካሬ ይሰጠዋል ተብሎ ይጠበቃል።
ከተሰሎንቄ የጎዳና ኳስ እስከ ኤምሬትስ
ክርስቶስ ዞሊስ (Christos Tzolis) ጥር 30 ቀን 2002 ዓ.ም በግሪክ በመፅሃፍ ቅዱስ የምናውቃት ታሪካዊቷ ከተማ ተሰሎንቄ (Thessaloniki) ተወለደ። ወላጆቹ ከአልባንያ የመጡ የኦርቶዶክስ ግሪካውያን ዘሮች (Greek minority) ሲሆኑ በጽኑ የሃይማኖት ባህልና በኦርቶዶክስ ክርስትና እሴቶች ውስጥ አድጓል።
«ክርስቶስ» የሚለው መጠሪያ ስሙም በግሪክ ኦርቶዶክስ እምነት ባህል መሠረት ከፍተኛ መንፈሳዊ ትርጉም ያለው ሲሆን በግል ህይወቱ እና በስፖርታዊ እንቅስቃሴዎቹ ውስጥ የእምነቱ ተጽዕኖ በግልጽ ይንጸባረቃል።
ዞሊስ ገና በ4 ዓመቱ ዶክሳ ፔንታሎፎስ በተባለ የአካባቢው አካዳሚ እግር ኳስ መጫወት የጀመረ ሲሆን በ2010 ወደ ሀገሪቱ ታላቅ ክለብ PAOK Thessaloniki ታዳጊ ቡድን ተቀላቀለ።
በ18 ዓመቱ በዋናው ቡድን ውስጥ ድንቅ ብቃቱን ማሳየት ጀመረ። በሁለት የውድድር ዘመናት ውስጥ በበ57 ጨዋታዎች 17 ግቦችን በማስቆጠር የዓመቱ ኮከብ ወጣት ተጫዋች እና የካፕ ውድድሩ ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪ በመሆን ድቅድቅ አቅሙን አሳየ።
በ2021 ኖርዊች ሲቲ በ11 ሚሊዮን ዩሮ ገደማ ወደ ፕሪመር ሊግ ቢያስፈርመውም በቂ የጨዋታ ዕድል ባለማግኘቱ ፈታኝ ጊዜ አሳለፈ (በኖርዊች እና በውሰት በኔዘርላንዱ ቴቨንቴ በድምሩ 45 ጨዋታዎች 6 ግቦች ብቻ)።
ሆኖም በ2023–24 የውድድር ዘመን በውሰት ወደ ጀርመኑ ፎርቱና ዱሰልዶርፍ ማምራቱ የሙያ ህይወቱን ሙሉ በሙሉ ለወጠው፦
በ30 የሊግ ጨዋታዎች 22 ግቦችን በማስቆጠር የ2ኛው ቡንደስሊጋ ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪ (Top Scorer) በመሆን አጠናቀቀ።
በ2024 ወደ ቤልጅየሙ ክለብ ብሩጅ (Club Brugge) የተዛወረው ዞሊስ፣ በአውሮፓ መድረክ ትልቅ ስም መገንባት ቻለ፦
2024–2026 (Club Brugge)በ108 ጨዋታዎች 43 ግቦችን አስቆጥሯል።
በተለይም ባለፈው የውድድር ዘመን በሁሉም ውድድሮች 22 ግቦችን በማስቆጠር እና 29 ግቦችን አመቻችቶ በመስጠት (51 G/A) የቤልጅየም ሊግ የዓመቱ ኮከብ ተጫዋች (Player of the Season) ሽልማትን አሸንፏል።
በቻምፒየንስ ሊግም ቢሆን በዋና ዋና ቡድኖች ላይ ያስቆጠራቸው ግቦች የትልልቅ ክለቦችን ትኩረት ስበዋል።
በ2020 ገና በ18 ዓመቱ የብሔራዊ ቡድኑን ማልያ የለበሰ ሲሆን በታሪክ 7ኛው ትንሹ ተጫዋች ሆኖ ተመዝግቧል። እስካሁን ለግሪክ በ20+ ጨዋታዎች ተሰልፎ 5+ ግቦችን አስቆጥሯል።
በሚኬል አርቴታ ጥራት ያለው የግራ መስመር አጥቂ ፍለጋ መሠረትአርሰናል በ£34 ሚሊዮን ክፍያ አስፈርሞታል። በፈጣን ድሪብሊንግ፣ ከሳጥን ውጭ በሚመታቸው ጠንካራ ኳሶች እና በስብዕናው አርሰናልን በግራ መስመር ትልቅ ጥንካሬ ይሰጠዋል ተብሎ ይጠበቃል።
13 days ago
ቼልሲ አሜሪካ ደርሷል
#ethiopia | የለንደኑ ክለብ ቼልሲ የወደፊት የቡድኑን አቅም ለመገንባት በሚያደርገው እንቅስቃሴ አሜሪካዊውን ድንቅ ታዳጊ መስመር ተጫዋች ቤንጂ ፍላወርስን ከአሜሪካው ዳላስ ኤፍሲ ለማስፈረም ከመሰረታዊ ስምምነት ላይ ደርሷል።
በተዘጋጀው የዝውውር እቅድ መሠረት ይህ የክንፍ መስመር ተወርዋሪ ዕድሜው 18 ዓመት እንደሞላ በቀጥታ ወደ ስታምፎርድ ብሪጅ በማምራት የቼልሲን አካዳሚ ይቀላቀላል።
በአሜሪካ እግር ኳስ ውስጥ ከሚገኙ እጅግ ተስፋ ሰጪ ታዳጊዎች አንዱ እንደሆነ የሚነገሩለትን ፍላወርስን ለማስፈረም በርካታ የአውሮፓ ታላላቅ ክለቦች የረጅም ጊዜ ፍላጎት አሳይተው የነበረ ቢሆንም ቼልሲዎች ፈጣን እንቅስቃሴ እያደረጉ ነው።
በያፌት ገ/ህይወት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#ethiopia | የለንደኑ ክለብ ቼልሲ የወደፊት የቡድኑን አቅም ለመገንባት በሚያደርገው እንቅስቃሴ አሜሪካዊውን ድንቅ ታዳጊ መስመር ተጫዋች ቤንጂ ፍላወርስን ከአሜሪካው ዳላስ ኤፍሲ ለማስፈረም ከመሰረታዊ ስምምነት ላይ ደርሷል።
በተዘጋጀው የዝውውር እቅድ መሠረት ይህ የክንፍ መስመር ተወርዋሪ ዕድሜው 18 ዓመት እንደሞላ በቀጥታ ወደ ስታምፎርድ ብሪጅ በማምራት የቼልሲን አካዳሚ ይቀላቀላል።
በአሜሪካ እግር ኳስ ውስጥ ከሚገኙ እጅግ ተስፋ ሰጪ ታዳጊዎች አንዱ እንደሆነ የሚነገሩለትን ፍላወርስን ለማስፈረም በርካታ የአውሮፓ ታላላቅ ክለቦች የረጅም ጊዜ ፍላጎት አሳይተው የነበረ ቢሆንም ቼልሲዎች ፈጣን እንቅስቃሴ እያደረጉ ነው።
በያፌት ገ/ህይወት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
15 days ago
የእናቱን ኑዛዜ ያከበረው ታዳጊ በሀዘን ውስጥ ሆኖ የተፈተነውን ፈተና በጥሩ ውጤት ወደ 9ኛ ክፍል ተዘዋወረ
ካሊድ የክልላዊ ፈተና በሚፈተንበት ወቅት እናቱ በፅኑ ታመው "በምንም ምክንያት ትምህርትህን እንዳታቋርጥ" በማለት ቃል አስገብተውት ነበር።
ካሊድ የክልላዊ ፈተና በሚፈተንበት ወቅት እናቱ በፅኑ ታመው "በምንም ምክንያት ትምህርትህን እንዳታቋርጥ" በማለት ቃል አስገብተውት ነበር።
Sponsored by
Surafel
15 days ago
ኤሌክትሮኒክስ ላይ ረጅም ሰዓት የሚያሳልፉ የልዩ ፍላጎት ልጆች የንግግር እና የመግባባት ክህሎታቸውን ሊጎዳ እንደሚችል ተነገረ
ልዩ ፍላጎት የሚያስፈልጋቸው ታዳጊዎች በቤት ውስጥ ረጅም ጊዜን በሚያሳልፋበት የክረምት ወቅት ላይ ቴሌቭዥንን ጨምሮ ከሌሎች የኤሌክትሮኒክስ ነገሮች መራቅ ይኖርባቸዋል። ልዩ ፍላጎት ያላቸው ልጆች ለአእምሮ እድገታቸው እንቅስቃሴ ያሏቸው ጨዋታዎችን እንዲጫወቱ ፣ በአእምሮ የሚሰሩና የሚገጣጠሙ መጫዎቻዎች ላይ ትኩረት እንዲያደርጉ ማገዝ ያስፈልጋል ሲሉ የፍቅር ኢትዮጵያ የአእምሮ ዕድገት ውስንነት ብሔራዊ ማህበር ዋና ስራ አስኪያጅ ወ/ሮ ሸዋጌጥ ክብረት ከብስራት ሬዲዮ ጋር በነበራቸው ቆይታ ገልጸዋል።
ልዩ ፍላጎት ያላቸው ታዳጊዎች ትምህርት ቤት ስለሄዱ ብቻ ውጤታማ መሆን ስለማይችሉ ብቻቸውን ከማዋል ይልቅ ልጆች ያሉባቸው እንዲሁም ሊደሰቱባቸው የሚችሉባቸው ቦታዎች ላይ እንዲሆኑ ማድረግ የመግባባት ክህሎታቸውን ለማዳበር ያግዛል። ከቴሌቪዥን እና ከሞባይል ጋር ረጅም ሰዓትን የሚያጠፉ የልዩ ፍላጎት ልጆች ከንግግር እና ከመግባባት ችሎታ ወደ ኋላ እንዲቀሩ ያደርጋቸዋል።
ይህ አይነቱ ችግር ያለባቸው ልጆች ንዴታቸውን የሚገልጹት ራሳቸውን በመጉዳት ሊሆን ስለሚችል ከልጅነት ጀምሮ በሚኖራቸው አስተዳደግ ላይ ከፍተኛ ትኩረት ማድረግ እና ሊያናድዳቸዉ የሚችሉ ነገሮችን መቅረፍ ያስፈልጋል።ዋና ስራ አስኪያጇ አክለውም ወላጆች ይህን ህመም የማመን ችግር እንደሚገጥማቸው ገልፀው፤ ስልጠና በመውሰድ ለዚህ ጉዳይ መፍትሄ ማግኘት እንደሚችሉ ጨምረው ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል።
Seledadotio
Seledadotio
ልዩ ፍላጎት የሚያስፈልጋቸው ታዳጊዎች በቤት ውስጥ ረጅም ጊዜን በሚያሳልፋበት የክረምት ወቅት ላይ ቴሌቭዥንን ጨምሮ ከሌሎች የኤሌክትሮኒክስ ነገሮች መራቅ ይኖርባቸዋል። ልዩ ፍላጎት ያላቸው ልጆች ለአእምሮ እድገታቸው እንቅስቃሴ ያሏቸው ጨዋታዎችን እንዲጫወቱ ፣ በአእምሮ የሚሰሩና የሚገጣጠሙ መጫዎቻዎች ላይ ትኩረት እንዲያደርጉ ማገዝ ያስፈልጋል ሲሉ የፍቅር ኢትዮጵያ የአእምሮ ዕድገት ውስንነት ብሔራዊ ማህበር ዋና ስራ አስኪያጅ ወ/ሮ ሸዋጌጥ ክብረት ከብስራት ሬዲዮ ጋር በነበራቸው ቆይታ ገልጸዋል።
ልዩ ፍላጎት ያላቸው ታዳጊዎች ትምህርት ቤት ስለሄዱ ብቻ ውጤታማ መሆን ስለማይችሉ ብቻቸውን ከማዋል ይልቅ ልጆች ያሉባቸው እንዲሁም ሊደሰቱባቸው የሚችሉባቸው ቦታዎች ላይ እንዲሆኑ ማድረግ የመግባባት ክህሎታቸውን ለማዳበር ያግዛል። ከቴሌቪዥን እና ከሞባይል ጋር ረጅም ሰዓትን የሚያጠፉ የልዩ ፍላጎት ልጆች ከንግግር እና ከመግባባት ችሎታ ወደ ኋላ እንዲቀሩ ያደርጋቸዋል።
ይህ አይነቱ ችግር ያለባቸው ልጆች ንዴታቸውን የሚገልጹት ራሳቸውን በመጉዳት ሊሆን ስለሚችል ከልጅነት ጀምሮ በሚኖራቸው አስተዳደግ ላይ ከፍተኛ ትኩረት ማድረግ እና ሊያናድዳቸዉ የሚችሉ ነገሮችን መቅረፍ ያስፈልጋል።ዋና ስራ አስኪያጇ አክለውም ወላጆች ይህን ህመም የማመን ችግር እንደሚገጥማቸው ገልፀው፤ ስልጠና በመውሰድ ለዚህ ጉዳይ መፍትሄ ማግኘት እንደሚችሉ ጨምረው ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል።
Seledadotio
Seledadotio
15 days ago
በኮንታ ልዩ ወረዳ እናትን ገድሎ ልጃቸውን የደፈረው ግለሰብ በሞት እንዲቀጣ ተወሰነ
በኮንታ ልዩ ወረዳ የግንባ አጋሬ ቀበሌ ነዋሪ የሆነው ተከሳሽ አብርሃም አመለ ቦንጆሬ፣ በፈጸማቸው ሶስት ከባድ ወንጀሎች በሞት እንዲቀጣ የኮንታ ልዩ ወረዳ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ውሳኔ አስተላለፈ።
ተከሳሹ ግንቦት 25 ቀን 2018 ዓ.ም ከገበያ ስትመለስ የነበረችውን የ15 ዓመት ታዳጊ ጠልፎ ወደ ጫካ በመውሰድ ሊደፍራት ሲታገል፣ የልጇን ጩኸት ሰምታ የደረሰችውን እናት ወይዘሮ አይናቴ ኬቶን በጩቤ ወግቶ በመግደል ገደል ውስጥ ወርውሯታል።
ተከሳሹ እናትን በዚህ አሰቃቂ ሁኔታ ካደባየ በኋላ የጠለፋትን ታዳጊ ልጅ አስገድዶ መድፈሩን የፖሊስ የምርመራ ውጤት እና የዐቃቤ ህግ ማስረጃዎች አረጋግጠዋል።
በመሆኑም ፍርድ ቤቱ በሐምሌ 1 ቀን 2018 ዓ.ም ባስቻለው ችሎት፣ ተከሳሹ በፈጸማቸው በጭካኔ የመግደል፣ በታዳጊ ልጅ ጠለፋ እና በአስገድዶ መድፈር ወንጀሎች ጥፋተኛ በማለቱ የሞት ቅጣት እንዲወሰንበት አድርጓል።
Seledadotio
Seledadotio
በኮንታ ልዩ ወረዳ የግንባ አጋሬ ቀበሌ ነዋሪ የሆነው ተከሳሽ አብርሃም አመለ ቦንጆሬ፣ በፈጸማቸው ሶስት ከባድ ወንጀሎች በሞት እንዲቀጣ የኮንታ ልዩ ወረዳ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ውሳኔ አስተላለፈ።
ተከሳሹ ግንቦት 25 ቀን 2018 ዓ.ም ከገበያ ስትመለስ የነበረችውን የ15 ዓመት ታዳጊ ጠልፎ ወደ ጫካ በመውሰድ ሊደፍራት ሲታገል፣ የልጇን ጩኸት ሰምታ የደረሰችውን እናት ወይዘሮ አይናቴ ኬቶን በጩቤ ወግቶ በመግደል ገደል ውስጥ ወርውሯታል።
ተከሳሹ እናትን በዚህ አሰቃቂ ሁኔታ ካደባየ በኋላ የጠለፋትን ታዳጊ ልጅ አስገድዶ መድፈሩን የፖሊስ የምርመራ ውጤት እና የዐቃቤ ህግ ማስረጃዎች አረጋግጠዋል።
በመሆኑም ፍርድ ቤቱ በሐምሌ 1 ቀን 2018 ዓ.ም ባስቻለው ችሎት፣ ተከሳሹ በፈጸማቸው በጭካኔ የመግደል፣ በታዳጊ ልጅ ጠለፋ እና በአስገድዶ መድፈር ወንጀሎች ጥፋተኛ በማለቱ የሞት ቅጣት እንዲወሰንበት አድርጓል።
Seledadotio
Seledadotio
17 days ago
በሳዑዲ ዓረቢያ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የነበሩ ከ1ሺህ 4መቶ በላይ ኢትዮጵያውያን ወደ ሀገራቸው ተመልሰዋል ተባለ
በሳምንቱ ውስጥ በተደረገ 6 ዙር በረራ 1ሺህ 4መቶ 81 ኢትዮጵያዊያን መመለሳቸዉን የሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታዉቋ፡፡
የተመለሱት 8መቶ79 ወንዶች፣ 5መቶ54 ሴቶች እና 48 ጨቅላ ህፃናት ሲሆኑ፤ከተመላሾች መካከል 82 እድሜያቸው ከአስራ ስምንት አመት በታች የሆኑ ታዳጊዎች ይገኙበታል።
መስከረም 5/ 2018 በተጀመረው ዜጎችን ወደ ሀገር ቤት የመመለስ ስራ እስካሁን ከ87 ሺህ በላይ ኢትዮጵያውያንን ወደ ሀገር መመለስ ተችሏል ተብሏል።
ሚኒስቴሩ ለተመላሽ ዜጎች በአየር ማረፊያና በማቆያ ማዕከላት ተገቢውን ድጋፍ እና እንክብካቤ የማድረግ እና ከቤተሰብ ጋር የማቀላቀል ስራ ከሚመለከታቸው ባለድርሻና አጋር አካላት ጋር በመተባበር በትኩረት እየሰራ እንደሚገኝ አስታዉቋል፡፡
በተጨማሪም መደበኛ ባልሆነ ፍልሰት ወደ ተለያዩ ሀገራት ሄደው የሚመለሱ የፍልሰት ተጎጂዎችን ለመደገፍና መልሶ ለማቋቋም የሚያስችሉ ተግባራትን በትብብር እያከናወነ መሆኑን ገልጿል፡፡
ወደፊትም በህገወጥ የሰዎች ዝውውር አስከፊነት ዙሪያ ህብረተሰቡን ለማስገንዘብ፣ መደበኛ ያልሆነ ፍልሰትን ለመከላከልና ደህንነቱ የተጠበቀ ፍልሰትን ለማበረታታት ሚኒስቴሩ የጀመራቸውን ስራዎች አጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን ተናግሯል፡፡
Seledadotio
Seledadotio
በሳምንቱ ውስጥ በተደረገ 6 ዙር በረራ 1ሺህ 4መቶ 81 ኢትዮጵያዊያን መመለሳቸዉን የሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታዉቋ፡፡
የተመለሱት 8መቶ79 ወንዶች፣ 5መቶ54 ሴቶች እና 48 ጨቅላ ህፃናት ሲሆኑ፤ከተመላሾች መካከል 82 እድሜያቸው ከአስራ ስምንት አመት በታች የሆኑ ታዳጊዎች ይገኙበታል።
መስከረም 5/ 2018 በተጀመረው ዜጎችን ወደ ሀገር ቤት የመመለስ ስራ እስካሁን ከ87 ሺህ በላይ ኢትዮጵያውያንን ወደ ሀገር መመለስ ተችሏል ተብሏል።
ሚኒስቴሩ ለተመላሽ ዜጎች በአየር ማረፊያና በማቆያ ማዕከላት ተገቢውን ድጋፍ እና እንክብካቤ የማድረግ እና ከቤተሰብ ጋር የማቀላቀል ስራ ከሚመለከታቸው ባለድርሻና አጋር አካላት ጋር በመተባበር በትኩረት እየሰራ እንደሚገኝ አስታዉቋል፡፡
በተጨማሪም መደበኛ ባልሆነ ፍልሰት ወደ ተለያዩ ሀገራት ሄደው የሚመለሱ የፍልሰት ተጎጂዎችን ለመደገፍና መልሶ ለማቋቋም የሚያስችሉ ተግባራትን በትብብር እያከናወነ መሆኑን ገልጿል፡፡
ወደፊትም በህገወጥ የሰዎች ዝውውር አስከፊነት ዙሪያ ህብረተሰቡን ለማስገንዘብ፣ መደበኛ ያልሆነ ፍልሰትን ለመከላከልና ደህንነቱ የተጠበቀ ፍልሰትን ለማበረታታት ሚኒስቴሩ የጀመራቸውን ስራዎች አጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን ተናግሯል፡፡
Seledadotio
Seledadotio
18 days ago
እንኳን ለቅዱስ ሚካኤል ወርሃዊ በዓል አደረሳችሁ፤ አደረሰን🙏 የቅዱስ ሚካኤል ምልጃ እና ረድኤት አይለየን!!!
ቅዱሳት መጻሕፍት እንደሚነግሩን የመላእክት ሁሉ አለቃቸው ቅዱስ ሚካኤል በፈጣሪው ኃይል ብዙ ድንቆችን ሠርቷል፡፡ ከመጀመሪያው ሰው አዳም ጀምሮ እስከ ዛሬ ድረስ አምነው ለሚጠሩት ረዳት ነው፡፡ በመዝሙር 33÷7 እደተጻፈው ዘወትርም ያድናቸው ዘንድ በሚፈሩት ሰዎች ዙሪያ ይሠፍራል፡፡ እግራችን እንዳይሰናከል ዘወትር ይጠብቀናል፡፡ የቅዱስ ሚካኤል ስሙ ድንቅ ነው፡፡ ነቢዩ ቅዱስ ዳንኤል እንደተናገረው ከእርሱ በቀርስ የሚያጸና ማን አለና! ለሕዝቡም የሚቆም ታዳጊ መልአክ ነው፡፡ ይህ ድንቅ መልአክ ከሺህ ዓመታት በፊት በሮም ከተማ ይህንን ድንቅ ተአምር መስከረም ዘጠኝ ቀን መሥራቱን ቤተ ክርስቲያን ትመሰክራለች፡፡ በቀድሞው የሮም ግዛት 'ሩፍምያ' የምትባል ከተማ ነበረች፡፡
ይህች ከተማ በእምነታቸው ጠንካሮች የሆኑ ጥቂት ክርስቲያኖችና በርካታ ኢአማንያን ተቀላቅለው የሚኖሩባት ናት፡፡ በተለይ ደግሞ የቤተ ክርስቲያኗ መጋቢ ፍጹም የእምነት ሰው ነበር፡፡ በቦታው የቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን በመኖሩም ብዙ ተአምራት ይደረግ ስለነበር ተበለጥን የሚል ስሜት የተሰማቸው አሕዛብ “ዮናናውያን”ይሕንን ቤተ ክርስቲያን ለማጥፋት ተማማሉ፡፡ በቀጥታ ሔደው ቢያፈርሱት ወይም ቢያቃጥሉት በሕግ እንደሚጠየቁ ያውቃሉና በሥጋዊ ጭንቅላታቸው ዘዴ ያሉትን መከሩና ወሰኑ፡፡ በከተማዋ ዳር የሚያልፍ አንድ ትልቅ ወንዝ አለ፡፡ በሞላ ጊዜ ያገኘውን ሁሉ ጠርጐ የሚወስድም ነበር፡፡ ታዲያ ክፋተኞቹ ሌሊት ሌሊት እየተነሱ የሚሔድበትን መንገድ ዘግተው ወደ ቤተ ክርስቲያኑ አቅጣጫ መንገድ ከፈቱለት ከቀናት በኋላ ከባድ ዝናብ በዚህች ቀን ጣለ፡፡
ወንዙ ትልቅ ነውና ያገኘውን ሁሉ እያገላበጠ ደረሰ፡፡ በወቅቱ በቅዱሱ መልአክ ቤተ መቅደስ ውስጥ ከመጋቢው በስተቀር ሰው አልነበረምና አስፈሪ ድምጽ ሰምቶ ሲወጣ ወንዙ እየደነፋ ወደ ቤተ ክርስቲያኑ እየመጣ ነው፡፡ ከደቂቃዎች በሁዋላ ቤተ ክርስቲያኑ እንዳልነበረ እንደሚሆን የተረዳው መጋቢ በታላቅ ድንግጤ ውስጥ ወደቀ፡፡ እርሱ አንድ ተስፋ ነበረውና ወደ ውስጥ ገብቶ በመላዕክት አለቃ በቅዱስ ሚካኤል ምስለ ስዕል ፊት ወድቆ ተማጸነ፡፡ ታላቁ ወንዝ ቤተ ክርስቲያኑን ጠርጎ የሚወወስደው ከሆነም የሚሆነውን ነገር ለመቀበልና ከዚያም ላለመውጣትም ወሰነ፡፡ ትንሽ ቆይቶ በታላቅ ኃይል ወንዙ ደረሰ፡፡ በዚህ ጊዜ የመላዕክት ሁሉ አለቃቸው ለጠራውም ፈጥኖ የሚደርሰው ቅዱስ ሚካኤል በግርማ ከሰማይ ወርዶ በወንዙ ፊት ቆመ፡፡
መጋቢውንም "ጽና አትፍራ፣ እኔ ካንተ ጋር ነኝና" ብሎት በያዘው የብርሃን በትረ-መስቀል መሬትን አንድ ጊዜ መታት፡፡ በዚያች ቅጽበትም ትልቅ ሸለቆ ተፈጠረ፡፡ በአስፈሪ ሁኔታ ሲመጣ የነበረው ወንዝም በሸለቆው ውስጥ አልፎ ሔደ፡፡ የሚገርመው ነገር የመላዕክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል ሸለቆው የተፈጠረው ከቤተ ክርስቲያኑ በታች መሆኑ ነው፡፡ ቤተክርስቲያኑ ግን ጸንቶ ቆመ፡፡ መጋቢውም እግዚአብሔርንና ቅዱስ ሚካኤልን አመሰገነ፡፡ ቅዱስ ሚካኤል መጋቢውን ባርኮት በክብር ዐረገ፡፡ በማግስቱ ክርስቲያኖቹ ይህንን አይተው ደስ አላቸው፣ መልአኩንም አከበሩት፣ አሕዛብ ግን አፈሩ፡፡
ራሳቸውን ለእግዚአብሔር ያስገዙ ገዳማውያንና ቅዱሳን ጸሎታቸው ኃይልን ታደርጋለች፡፡ ገዳማቸውን እየደገፍን በዓታቸውን እያጸናን የበረከታቸው ተሳታፊ እንሁን፡፡
ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም
ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391
ወይም
አቢሲኒያ ባንክ
141029444
የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444
ቅዱሳት መጻሕፍት እንደሚነግሩን የመላእክት ሁሉ አለቃቸው ቅዱስ ሚካኤል በፈጣሪው ኃይል ብዙ ድንቆችን ሠርቷል፡፡ ከመጀመሪያው ሰው አዳም ጀምሮ እስከ ዛሬ ድረስ አምነው ለሚጠሩት ረዳት ነው፡፡ በመዝሙር 33÷7 እደተጻፈው ዘወትርም ያድናቸው ዘንድ በሚፈሩት ሰዎች ዙሪያ ይሠፍራል፡፡ እግራችን እንዳይሰናከል ዘወትር ይጠብቀናል፡፡ የቅዱስ ሚካኤል ስሙ ድንቅ ነው፡፡ ነቢዩ ቅዱስ ዳንኤል እንደተናገረው ከእርሱ በቀርስ የሚያጸና ማን አለና! ለሕዝቡም የሚቆም ታዳጊ መልአክ ነው፡፡ ይህ ድንቅ መልአክ ከሺህ ዓመታት በፊት በሮም ከተማ ይህንን ድንቅ ተአምር መስከረም ዘጠኝ ቀን መሥራቱን ቤተ ክርስቲያን ትመሰክራለች፡፡ በቀድሞው የሮም ግዛት 'ሩፍምያ' የምትባል ከተማ ነበረች፡፡
ይህች ከተማ በእምነታቸው ጠንካሮች የሆኑ ጥቂት ክርስቲያኖችና በርካታ ኢአማንያን ተቀላቅለው የሚኖሩባት ናት፡፡ በተለይ ደግሞ የቤተ ክርስቲያኗ መጋቢ ፍጹም የእምነት ሰው ነበር፡፡ በቦታው የቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን በመኖሩም ብዙ ተአምራት ይደረግ ስለነበር ተበለጥን የሚል ስሜት የተሰማቸው አሕዛብ “ዮናናውያን”ይሕንን ቤተ ክርስቲያን ለማጥፋት ተማማሉ፡፡ በቀጥታ ሔደው ቢያፈርሱት ወይም ቢያቃጥሉት በሕግ እንደሚጠየቁ ያውቃሉና በሥጋዊ ጭንቅላታቸው ዘዴ ያሉትን መከሩና ወሰኑ፡፡ በከተማዋ ዳር የሚያልፍ አንድ ትልቅ ወንዝ አለ፡፡ በሞላ ጊዜ ያገኘውን ሁሉ ጠርጐ የሚወስድም ነበር፡፡ ታዲያ ክፋተኞቹ ሌሊት ሌሊት እየተነሱ የሚሔድበትን መንገድ ዘግተው ወደ ቤተ ክርስቲያኑ አቅጣጫ መንገድ ከፈቱለት ከቀናት በኋላ ከባድ ዝናብ በዚህች ቀን ጣለ፡፡
ወንዙ ትልቅ ነውና ያገኘውን ሁሉ እያገላበጠ ደረሰ፡፡ በወቅቱ በቅዱሱ መልአክ ቤተ መቅደስ ውስጥ ከመጋቢው በስተቀር ሰው አልነበረምና አስፈሪ ድምጽ ሰምቶ ሲወጣ ወንዙ እየደነፋ ወደ ቤተ ክርስቲያኑ እየመጣ ነው፡፡ ከደቂቃዎች በሁዋላ ቤተ ክርስቲያኑ እንዳልነበረ እንደሚሆን የተረዳው መጋቢ በታላቅ ድንግጤ ውስጥ ወደቀ፡፡ እርሱ አንድ ተስፋ ነበረውና ወደ ውስጥ ገብቶ በመላዕክት አለቃ በቅዱስ ሚካኤል ምስለ ስዕል ፊት ወድቆ ተማጸነ፡፡ ታላቁ ወንዝ ቤተ ክርስቲያኑን ጠርጎ የሚወወስደው ከሆነም የሚሆነውን ነገር ለመቀበልና ከዚያም ላለመውጣትም ወሰነ፡፡ ትንሽ ቆይቶ በታላቅ ኃይል ወንዙ ደረሰ፡፡ በዚህ ጊዜ የመላዕክት ሁሉ አለቃቸው ለጠራውም ፈጥኖ የሚደርሰው ቅዱስ ሚካኤል በግርማ ከሰማይ ወርዶ በወንዙ ፊት ቆመ፡፡
መጋቢውንም "ጽና አትፍራ፣ እኔ ካንተ ጋር ነኝና" ብሎት በያዘው የብርሃን በትረ-መስቀል መሬትን አንድ ጊዜ መታት፡፡ በዚያች ቅጽበትም ትልቅ ሸለቆ ተፈጠረ፡፡ በአስፈሪ ሁኔታ ሲመጣ የነበረው ወንዝም በሸለቆው ውስጥ አልፎ ሔደ፡፡ የሚገርመው ነገር የመላዕክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል ሸለቆው የተፈጠረው ከቤተ ክርስቲያኑ በታች መሆኑ ነው፡፡ ቤተክርስቲያኑ ግን ጸንቶ ቆመ፡፡ መጋቢውም እግዚአብሔርንና ቅዱስ ሚካኤልን አመሰገነ፡፡ ቅዱስ ሚካኤል መጋቢውን ባርኮት በክብር ዐረገ፡፡ በማግስቱ ክርስቲያኖቹ ይህንን አይተው ደስ አላቸው፣ መልአኩንም አከበሩት፣ አሕዛብ ግን አፈሩ፡፡
ራሳቸውን ለእግዚአብሔር ያስገዙ ገዳማውያንና ቅዱሳን ጸሎታቸው ኃይልን ታደርጋለች፡፡ ገዳማቸውን እየደገፍን በዓታቸውን እያጸናን የበረከታቸው ተሳታፊ እንሁን፡፡
ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም
ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391
ወይም
አቢሲኒያ ባንክ
141029444
የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444
Sponsored by
Surafel
18 days ago
🏃♀️🏃♂️ የ2018 ኢትዮ ቴሌኮም ታላቁ ሩጫ በሐረር በድምቀት ተካሔደ!!
መነሻና መድረሻውን ሐረር በር ላይ በማድረግ ፕሮፌሽናል አትሌቶችና ከአዲስ አባባ ተጓዥ ተሳታፊዎችን ያካተተ ልዩ የ10ኪ.ሜ ውድድር በወንዶችና በሴቶች ደስ በሚል ድባብ ተካሒዷል።
በተጨማሪም ተተኪዎችን ለማፍራት ከ16 ዓመት በታች ታዳጊ አትሌቶች የተሳተፉበት የ1.5 ኪ.ሜ ውድድርና ከ11 ዓመት በታች ልጆች የተሳተፉበት የ1 ኪ.ሜ.ውድድር ሌላው የዕለቱ ድምቀት ነበር፡፡
የአገራችን አትሌቲክስ ለማሳደግና ተተኪዎች ለማፍራት በሚደረገው ጥረት ኩባንያችን ኢትዮ ቴሌኮም በስያሜና የቴክኖሎጂ አጋርነት ከታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ጋር እየሠራ የሚገኝ ሲሆን ወደ ፊትም በአትሌቲክሱ ዘርፍ የምናደርገውን አስተዋጽኦ አጠናክረን እንቀጥላለን።
#ethiotelecomgreathararrun #greatethiopianrun #harar #telebirr #ethiotelecom
መነሻና መድረሻውን ሐረር በር ላይ በማድረግ ፕሮፌሽናል አትሌቶችና ከአዲስ አባባ ተጓዥ ተሳታፊዎችን ያካተተ ልዩ የ10ኪ.ሜ ውድድር በወንዶችና በሴቶች ደስ በሚል ድባብ ተካሒዷል።
በተጨማሪም ተተኪዎችን ለማፍራት ከ16 ዓመት በታች ታዳጊ አትሌቶች የተሳተፉበት የ1.5 ኪ.ሜ ውድድርና ከ11 ዓመት በታች ልጆች የተሳተፉበት የ1 ኪ.ሜ.ውድድር ሌላው የዕለቱ ድምቀት ነበር፡፡
የአገራችን አትሌቲክስ ለማሳደግና ተተኪዎች ለማፍራት በሚደረገው ጥረት ኩባንያችን ኢትዮ ቴሌኮም በስያሜና የቴክኖሎጂ አጋርነት ከታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ጋር እየሠራ የሚገኝ ሲሆን ወደ ፊትም በአትሌቲክሱ ዘርፍ የምናደርገውን አስተዋጽኦ አጠናክረን እንቀጥላለን።
#ethiotelecomgreathararrun #greatethiopianrun #harar #telebirr #ethiotelecom
18 days ago
🏃♀️🏃♂️ የ2018 ኢትዮ ቴሌኮም ታላቁ ሩጫ በሐረር በድምቀት ተካሔደ!!
መነሻና መድረሻውን ሐረር በር ላይ በማድረግ ፕሮፌሽናል አትሌቶችና ከአዲስ አባባ ተጓዥ ተሳታፊዎችን ያካተተ ልዩ የ10ኪ.ሜ ውድድር በወንዶችና በሴቶች ደስ በሚል ድባብ ተካሒዷል።
በተጨማሪም ተተኪዎችን ለማፍራት ከ16 ዓመት በታች ታዳጊ አትሌቶች የተሳተፉበት የ1.5 ኪ.ሜ ውድድርና ከ11 ዓመት በታች ልጆች የተሳተፉበት የ1 ኪ.ሜ.ውድድር ሌላው የዕለቱ ድምቀት ነበር፡፡
የአገራችን አትሌቲክስ ለማሳደግና ተተኪዎች ለማፍራት በሚደረገው ጥረት ኩባንያችን ኢትዮ ቴሌኮም በስያሜና የቴክኖሎጂ አጋርነት ከታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ጋር እየሠራ የሚገኝ ሲሆን ወደ ፊትም በአትሌቲክሱ ዘርፍ የምናደርገውን አስተዋጽኦ አጠናክረን እንቀጥላለን።
#ethiotelecomgreathararrun #greatethiopianrun #harar #telebirr #ethiotelecom
መነሻና መድረሻውን ሐረር በር ላይ በማድረግ ፕሮፌሽናል አትሌቶችና ከአዲስ አባባ ተጓዥ ተሳታፊዎችን ያካተተ ልዩ የ10ኪ.ሜ ውድድር በወንዶችና በሴቶች ደስ በሚል ድባብ ተካሒዷል።
በተጨማሪም ተተኪዎችን ለማፍራት ከ16 ዓመት በታች ታዳጊ አትሌቶች የተሳተፉበት የ1.5 ኪ.ሜ ውድድርና ከ11 ዓመት በታች ልጆች የተሳተፉበት የ1 ኪ.ሜ.ውድድር ሌላው የዕለቱ ድምቀት ነበር፡፡
የአገራችን አትሌቲክስ ለማሳደግና ተተኪዎች ለማፍራት በሚደረገው ጥረት ኩባንያችን ኢትዮ ቴሌኮም በስያሜና የቴክኖሎጂ አጋርነት ከታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ጋር እየሠራ የሚገኝ ሲሆን ወደ ፊትም በአትሌቲክሱ ዘርፍ የምናደርገውን አስተዋጽኦ አጠናክረን እንቀጥላለን።
#ethiotelecomgreathararrun #greatethiopianrun #harar #telebirr #ethiotelecom
Comments