Logo
Getu Temesgen
ቼልሲ አሜሪካ ደርሷል
#ethiopia | ​የለንደኑ ክለብ ቼልሲ የወደፊት የቡድኑን አቅም ለመገንባት በሚያደርገው እንቅስቃሴ አሜሪካዊውን ድንቅ ታዳጊ መስመር ተጫዋች ቤንጂ ፍላወርስን ከአሜሪካው ዳላስ ኤፍሲ ለማስፈረም ከመሰረታዊ ስምምነት ላይ ደርሷል።

በተዘጋጀው የዝውውር እቅድ መሠረት ይህ የክንፍ መስመር ተወርዋሪ ዕድሜው 18 ዓመት እንደሞላ በቀጥታ ወደ ስታምፎርድ ብሪጅ በማምራት የቼልሲን አካዳሚ ይቀላቀላል።

​በአሜሪካ እግር ኳስ ውስጥ ከሚገኙ እጅግ ተስፋ ሰጪ ታዳጊዎች አንዱ እንደሆነ የሚነገሩለትን ፍላወርስን ለማስፈረም በርካታ የአውሮፓ ታላላቅ ክለቦች የረጅም ጊዜ ፍላጎት አሳይተው የነበረ ቢሆንም ቼልሲዎች ፈጣን እንቅስቃሴ እያደረጉ ነው።

በያፌት ገ/ህይወት

Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu

12 days ago

No replys yet!

Be the first to share what you think — your comment will appear here.