13 hours ago
በጡረታ የተገለሉት አመራር ከፍተኛ ስልጣን ተሰጣቸው
*የቀድሞ የባህር ሀይሏ አመራሯ ጥቁር አሜሪካዊት ቁልፉን ተቋም ለመመራት ተሹመዋል።
#ethiopia |የአሜሪካ ሴኔት ባደረገው ምርጫ የቀድሞ የባህር ኃይል አባሏ
ዶ/ር ኤሪካ ሸዋርትዝ የአሜሪካ የበሽታዎች መከላከል እና መቆጣጠሪያ ማዕከል ዋና ዳይሬክተር አድርጎ መረጠ።
ይህ ሹመት ተቋሙ ላለፈው አንድ አመት ገደማ ያህል ያለ ቋሚ መሪ በጊዜያዊ አመራር ሲመራ ከቆየ በኋላ የተሰጠ ትልቁ ሹመት ነው ተብሏል።
የቀድሞ የባህር ሀይል አባል ዶክተር ኤሪካ በታሪክ ሲ.ዲ.ሲን በመሪነት የሚያገለግሉ የመጀመርያዋ ጥቁር አሜሪካዊት ሴት አድርጓቸዋል።
ዶክተር ኤሪካ በጡረታ የተገለሉ የባህር ኃይል አመራር የነበሩ ሲሆን ቀደም ሲል የአሜሪካ የባህር ሀይል የጤና ስርዓትን በበላይነት የመሩ ብቁ የህክምና እና የአመራር ባለሙያ መሆናቸው ታውቋል።
ላለፉት 12 ወራት ያህል ቋሚ ዳይሬክተር ሳይኖረው የቆየው ሲዲሲ ለተደቀኑበት ዓለም አቀፍ እና ሀገር አቀፍ የጤና ስጋቶች አዲስ እና ጠንካራ አመራር ለማግኘት ያደረገው ጥረት በመጨረሻም ውጤት አምጥቶለታል።
ሔኖክ ወ/ገብርኤል
#ethiopia #getutemesgen #getunews #usa #cdc #uscoastguard #drericaschwartz
*የቀድሞ የባህር ሀይሏ አመራሯ ጥቁር አሜሪካዊት ቁልፉን ተቋም ለመመራት ተሹመዋል።
#ethiopia |የአሜሪካ ሴኔት ባደረገው ምርጫ የቀድሞ የባህር ኃይል አባሏ
ዶ/ር ኤሪካ ሸዋርትዝ የአሜሪካ የበሽታዎች መከላከል እና መቆጣጠሪያ ማዕከል ዋና ዳይሬክተር አድርጎ መረጠ።
ይህ ሹመት ተቋሙ ላለፈው አንድ አመት ገደማ ያህል ያለ ቋሚ መሪ በጊዜያዊ አመራር ሲመራ ከቆየ በኋላ የተሰጠ ትልቁ ሹመት ነው ተብሏል።
የቀድሞ የባህር ሀይል አባል ዶክተር ኤሪካ በታሪክ ሲ.ዲ.ሲን በመሪነት የሚያገለግሉ የመጀመርያዋ ጥቁር አሜሪካዊት ሴት አድርጓቸዋል።
ዶክተር ኤሪካ በጡረታ የተገለሉ የባህር ኃይል አመራር የነበሩ ሲሆን ቀደም ሲል የአሜሪካ የባህር ሀይል የጤና ስርዓትን በበላይነት የመሩ ብቁ የህክምና እና የአመራር ባለሙያ መሆናቸው ታውቋል።
ላለፉት 12 ወራት ያህል ቋሚ ዳይሬክተር ሳይኖረው የቆየው ሲዲሲ ለተደቀኑበት ዓለም አቀፍ እና ሀገር አቀፍ የጤና ስጋቶች አዲስ እና ጠንካራ አመራር ለማግኘት ያደረገው ጥረት በመጨረሻም ውጤት አምጥቶለታል።
ሔኖክ ወ/ገብርኤል
#ethiopia #getutemesgen #getunews #usa #cdc #uscoastguard #drericaschwartz
24 hours ago
የኤቦላ ቫይረስ በአሳሳቢ ሁኔታ እየተሰራጨ ነው ሲል ድንበር የለሽ የሐኪሞች ቡድን አሳወቀ
የዛሬ ሁለት ወራት ተኩል ገደማ በኮንጎ የተከሰተው የኤቦላ ቫይረስ ወረርሽኝ በአሳሳቢና ባልተጠበቀ ሁኔታ በሀገሪቱ እየተሰራጨ ነው ሲል ድንበር የለሽ የሐኪሞች ቡድን በምህፃሩ MSF አስታወቀ።
ድርጅቱ እንደሚለው በሽታውን ለመከላከል የህክምና ባለሞያዎች ያላሰለሰ ጥረት እያደረጉ ቢሆንም፤ ወረርሽኙ ከመቼውም ጊዜ በበለጠ በአሳሳቢ ሁኔታ እየተሰራጨ ይገኛል።
እስካሁን ከ3 ሺህ 600 በላይ ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው በላቦራቶሪ ተረጋገጧል፤ ቁጥራቸው 1 ሺህ 500 የሚጠጋ ሰዎችም ሞተዋል።
በአሁኑ ጊዜ ዋናው ተግዳሮት ባለሥልጣናት በበሽታው ከተያዙ ሰዎች ጋር ግንኙነት ያላቸውን ሰዎች መለየት እንደተሳናቸው መሆኑ ነው።
ቡንያ በተባለው አካባቢ የሚገኝ የህክምና ማዕከል ውስጥ ከሚገኙት በሽተኞች ውስጥ 90 በመቶው ከዚህ ቀደም በኤቦላ ቫይረስ ከተያዙ ሰዎች ጋር ንክኪ እንዳላቸው የሚታወቅ ነገር የለም።
የዓለም የጤና ድርጅት ዋና ኃላፊ ዶክተር ቴዎድሮስ አድሃኖም ከመንግሥት ኃላፊዎችና ከሰብአዊ ድርጅቶች ጋር ለመነጋገር ዛሬ ወደ ኮንጎ ኪንሻሳ ሄደዋል።
ዶክተር ቴዎድሮስ የኤቦላ ወረርሽኝ ከተሰከሰተ ወዲህ ወደ ኮንጎ ሲጓዙ የዛሬው ለሁለተኛ ጊዜ ነው።
Seledadotio
Seledadotio
የዛሬ ሁለት ወራት ተኩል ገደማ በኮንጎ የተከሰተው የኤቦላ ቫይረስ ወረርሽኝ በአሳሳቢና ባልተጠበቀ ሁኔታ በሀገሪቱ እየተሰራጨ ነው ሲል ድንበር የለሽ የሐኪሞች ቡድን በምህፃሩ MSF አስታወቀ።
ድርጅቱ እንደሚለው በሽታውን ለመከላከል የህክምና ባለሞያዎች ያላሰለሰ ጥረት እያደረጉ ቢሆንም፤ ወረርሽኙ ከመቼውም ጊዜ በበለጠ በአሳሳቢ ሁኔታ እየተሰራጨ ይገኛል።
እስካሁን ከ3 ሺህ 600 በላይ ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው በላቦራቶሪ ተረጋገጧል፤ ቁጥራቸው 1 ሺህ 500 የሚጠጋ ሰዎችም ሞተዋል።
በአሁኑ ጊዜ ዋናው ተግዳሮት ባለሥልጣናት በበሽታው ከተያዙ ሰዎች ጋር ግንኙነት ያላቸውን ሰዎች መለየት እንደተሳናቸው መሆኑ ነው።
ቡንያ በተባለው አካባቢ የሚገኝ የህክምና ማዕከል ውስጥ ከሚገኙት በሽተኞች ውስጥ 90 በመቶው ከዚህ ቀደም በኤቦላ ቫይረስ ከተያዙ ሰዎች ጋር ንክኪ እንዳላቸው የሚታወቅ ነገር የለም።
የዓለም የጤና ድርጅት ዋና ኃላፊ ዶክተር ቴዎድሮስ አድሃኖም ከመንግሥት ኃላፊዎችና ከሰብአዊ ድርጅቶች ጋር ለመነጋገር ዛሬ ወደ ኮንጎ ኪንሻሳ ሄደዋል።
ዶክተር ቴዎድሮስ የኤቦላ ወረርሽኝ ከተሰከሰተ ወዲህ ወደ ኮንጎ ሲጓዙ የዛሬው ለሁለተኛ ጊዜ ነው።
Seledadotio
Seledadotio
24 hours ago
"በለጠ" - የድንች ዝርያ
#ethiopia | አዊ ብሔረሰብ አስተዳደር – አድማስ ሁለገብ የገበሬዎች የኅብረት ሥራ ማኅበራት ዩኒየን በአዊ ብሔረሰብ አስተዳደር የተሻሻሉ የድንች ዘሮችን በማባዛት የአርሶ አደሮችን ምርታማነትና ገቢ ለማሳደግ እየሰራ መሆኑን ገለጸ።
በአንከሻ ጓጉሳ ወረዳ ካፍታ ቀበሌ 20 ወጣቶች በሚያካሂዱት የድንች ዘር ብዜት ልማት ላይ የገበሬዎች በዓል ተካሂዷል።
የዩኒየኑ ዋና ሥራ አስኪያጅ መሠረት ወርቄ፣ በአካባቢው የድንች ምርጥ ዘር እጥረትን ለመቅረፍ የተሻሻሉ ዘሮችን የማባዛት ሥራ መጀመሩን ገልጸው፣ ከ1.5 ሄክታር የተጀመረው ፕሮጀክት በአሁኑ ወቅት በ6 ሄክታር መሬት በጓንጓ፣ ባንጃ፣ አንከሻ እና ጓጉሳ ሽኩዳድ ወረዳዎች መስፋፋቱን ጠቁመዋል።
እንደ መሠረት ወርቄ ገለጻ፣ ዩኒየኑ በቀጣይ ዓመት የዘር ብዜት ልማቱን ወደ 15 ሄክታር በማስፋት የድንች ሰብልን ከምግብነት ባለፈ ለኢንዱስትሪ ግብዓት እንዲሆን ለማድረግ እየሰራ ነው።
የአዊ ብሔረሰብ አስተዳደር ግብርና መምሪያ ኃላፊ ቤዛዊት ጌታሁን በበኩላቸው፣ ድንች ለምግብ ዋስትና ብቻ ሳይሆን ለኢኮኖሚ ዕድገትም ጠቃሚ ሰብል መሆኑን ገልጸው፣ የተሻሻሉ ዝርያዎችን ማስፋፋት ምርታማነትን ለማሳደግ ወሳኝ መሆኑን አስረድተዋል።
"በለጠ" የተሰኘው የድንች ዝርያ በሽታን የመቋቋም አቅም ያለው ሲሆን፣ በሄክታር እስከ 350 ኩንታል ምርት እንደሚሰጥ ተጠቁሟል።
#ethiopia | አዊ ብሔረሰብ አስተዳደር – አድማስ ሁለገብ የገበሬዎች የኅብረት ሥራ ማኅበራት ዩኒየን በአዊ ብሔረሰብ አስተዳደር የተሻሻሉ የድንች ዘሮችን በማባዛት የአርሶ አደሮችን ምርታማነትና ገቢ ለማሳደግ እየሰራ መሆኑን ገለጸ።
በአንከሻ ጓጉሳ ወረዳ ካፍታ ቀበሌ 20 ወጣቶች በሚያካሂዱት የድንች ዘር ብዜት ልማት ላይ የገበሬዎች በዓል ተካሂዷል።
የዩኒየኑ ዋና ሥራ አስኪያጅ መሠረት ወርቄ፣ በአካባቢው የድንች ምርጥ ዘር እጥረትን ለመቅረፍ የተሻሻሉ ዘሮችን የማባዛት ሥራ መጀመሩን ገልጸው፣ ከ1.5 ሄክታር የተጀመረው ፕሮጀክት በአሁኑ ወቅት በ6 ሄክታር መሬት በጓንጓ፣ ባንጃ፣ አንከሻ እና ጓጉሳ ሽኩዳድ ወረዳዎች መስፋፋቱን ጠቁመዋል።
እንደ መሠረት ወርቄ ገለጻ፣ ዩኒየኑ በቀጣይ ዓመት የዘር ብዜት ልማቱን ወደ 15 ሄክታር በማስፋት የድንች ሰብልን ከምግብነት ባለፈ ለኢንዱስትሪ ግብዓት እንዲሆን ለማድረግ እየሰራ ነው።
የአዊ ብሔረሰብ አስተዳደር ግብርና መምሪያ ኃላፊ ቤዛዊት ጌታሁን በበኩላቸው፣ ድንች ለምግብ ዋስትና ብቻ ሳይሆን ለኢኮኖሚ ዕድገትም ጠቃሚ ሰብል መሆኑን ገልጸው፣ የተሻሻሉ ዝርያዎችን ማስፋፋት ምርታማነትን ለማሳደግ ወሳኝ መሆኑን አስረድተዋል።
"በለጠ" የተሰኘው የድንች ዝርያ በሽታን የመቋቋም አቅም ያለው ሲሆን፣ በሄክታር እስከ 350 ኩንታል ምርት እንደሚሰጥ ተጠቁሟል።
1 day ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የሚኒሶታ ጤና መምሪያ በግዛቲቱ በሚገኙ የሜክሲኮ ምግብ ቤቶች ውስጥ ከሚቀርበው ሃላፒኖ የሚባለው የቃሪያ ዓይነት (የሜክሲኮ ቃሪያ) ጋር የተያያዘ የ'ሳልሞኔላ ጃቪያና' ወረርሽኝን እየመረመረ መሆኑን አስታወቀ። መምሪያው እስካሁን 110 የተረጋገጡ የሳልሞኔላ ታማሚዎች መመዝገባቸውን ገልጿል።
የጤና ባለስልጣናት ህመሙ ከተከሰተባቸው ሰዎች መካከል 84ቱን ያነጋገሩ ሲሆን፣ ከእነዚህ ውስጥ 75 በመቶ የሚሆኑት ከሰኔ 14 እስከ ሀምሌ 14 ባለው ጊዜ ውስጥ 'ቺፖትሌ' በተባለው ታዋቂ ምግብ ቤት የተመገቡ መሆናቸውን ጠቁመዋል። ቀሪዎቹ ደግሞ በሌሎች የሜክሲኮ ምግብ ቤቶች መመገባቸውን ተናግረዋል። ወረርሽኙን ተከትሎ ቺፖትሌ በሚኒሶታ ከሚገኙ በርካታ ቅርንጫፎቹ ሃላፔኖ ቃሪያዎችን ማንሳቱን አስታውቋል።
የቺፖትሌ ቃል አቀባይ በሰጡት መግለጫ፣ "ሊከሰት ስለሚችለው ወረርሽኝ እንደሰማን ወዲያውኑ የክትትል ስርዓታችንን በመጠቀም ሃላፔኖ ቃሪያው የተሰራጨባቸውን ምግብ ቤቶች ለይተናል፤ ለጥንቃቄ ሲባልም የተጠረጠሩትን ምርቶች ከምግብ ቤቶቻችን በማስወገድ ከሌሎች አምራቾች በተገኙ ቃሪያዎች ተክተናል" ብለዋል። በሚኒሶታ ጤና መምሪያ የምግብ ወለድ በሽታዎች ክፍል ከፍተኛ ኤፒዲሚዮሎጂስት ካርሎታ ሜዱስ በበኩላቸው፣ ቺፖትሌ ከምርመራው ጋር በተያያዘ መረጃዎችን ከመስጠት ጀምሮ የተጠረጠሩትን ቃሪያዎች ለማስወገድ የወሰደውን ፈጣን እርምጃ በማንሳት የተቋሙን ሙሉ ትብብር አድንቀዋል።
የጤና መምሪያው ወረርሽኙ አሁንም እንደቀጠለ ለማወቅ ጊዜው ገና መሆኑን ቢገልጽም፣ ቺፖትሌ በወሰደው ፈጣን እርምጃ ምክንያት በድርጅቱ ላይ ስጋት እንደሌለው አስታውቋል። ሆኖም የተበከለው ቃሪያ በሌሎች ምግብ ቤቶች አሁንም እየቀረበ ከሆነ ወረርሽኙ ሊቀጥል እንደሚችል እና በቀጣይ ቀናት ተጨማሪ ታማሚዎች ሊመዘገቡ እንደሚችሉ ስጋቱን አጋርቷል።
ወረርሽኙን በፍጥነት ለመቆጣጠር የታማሚዎች መረጃ እጅግ ወሳኝ መሆኑን የገለጹት ካርሎታ ሜዱስ፣ የጤና ባለሙያዎች ምርመራቸውን የሚያካሂዱት ጥቆማ በደረሳቸው ታማሚዎች ላይ በመደወል በመሆኑ፣ ህብረተሰቡ ለሚደረጉ የስልክ ጥሪዎች ምላሽ በመስጠት ትብብር እንዲያደርግ ጥሪያቸውን አቅርበዋል።
የጤና ባለስልጣናት ህመሙ ከተከሰተባቸው ሰዎች መካከል 84ቱን ያነጋገሩ ሲሆን፣ ከእነዚህ ውስጥ 75 በመቶ የሚሆኑት ከሰኔ 14 እስከ ሀምሌ 14 ባለው ጊዜ ውስጥ 'ቺፖትሌ' በተባለው ታዋቂ ምግብ ቤት የተመገቡ መሆናቸውን ጠቁመዋል። ቀሪዎቹ ደግሞ በሌሎች የሜክሲኮ ምግብ ቤቶች መመገባቸውን ተናግረዋል። ወረርሽኙን ተከትሎ ቺፖትሌ በሚኒሶታ ከሚገኙ በርካታ ቅርንጫፎቹ ሃላፔኖ ቃሪያዎችን ማንሳቱን አስታውቋል።
የቺፖትሌ ቃል አቀባይ በሰጡት መግለጫ፣ "ሊከሰት ስለሚችለው ወረርሽኝ እንደሰማን ወዲያውኑ የክትትል ስርዓታችንን በመጠቀም ሃላፔኖ ቃሪያው የተሰራጨባቸውን ምግብ ቤቶች ለይተናል፤ ለጥንቃቄ ሲባልም የተጠረጠሩትን ምርቶች ከምግብ ቤቶቻችን በማስወገድ ከሌሎች አምራቾች በተገኙ ቃሪያዎች ተክተናል" ብለዋል። በሚኒሶታ ጤና መምሪያ የምግብ ወለድ በሽታዎች ክፍል ከፍተኛ ኤፒዲሚዮሎጂስት ካርሎታ ሜዱስ በበኩላቸው፣ ቺፖትሌ ከምርመራው ጋር በተያያዘ መረጃዎችን ከመስጠት ጀምሮ የተጠረጠሩትን ቃሪያዎች ለማስወገድ የወሰደውን ፈጣን እርምጃ በማንሳት የተቋሙን ሙሉ ትብብር አድንቀዋል።
የጤና መምሪያው ወረርሽኙ አሁንም እንደቀጠለ ለማወቅ ጊዜው ገና መሆኑን ቢገልጽም፣ ቺፖትሌ በወሰደው ፈጣን እርምጃ ምክንያት በድርጅቱ ላይ ስጋት እንደሌለው አስታውቋል። ሆኖም የተበከለው ቃሪያ በሌሎች ምግብ ቤቶች አሁንም እየቀረበ ከሆነ ወረርሽኙ ሊቀጥል እንደሚችል እና በቀጣይ ቀናት ተጨማሪ ታማሚዎች ሊመዘገቡ እንደሚችሉ ስጋቱን አጋርቷል።
ወረርሽኙን በፍጥነት ለመቆጣጠር የታማሚዎች መረጃ እጅግ ወሳኝ መሆኑን የገለጹት ካርሎታ ሜዱስ፣ የጤና ባለሙያዎች ምርመራቸውን የሚያካሂዱት ጥቆማ በደረሳቸው ታማሚዎች ላይ በመደወል በመሆኑ፣ ህብረተሰቡ ለሚደረጉ የስልክ ጥሪዎች ምላሽ በመስጠት ትብብር እንዲያደርግ ጥሪያቸውን አቅርበዋል።
2 days ago
ብሩስ ዊሊስ ባለቤት የባለቤቷን ህመም (FTD) ለመከታተል የሚያስችል ህግ እንዲፀድቅ ግፊት አደረገች
የታዋቂው የፊልም ኮከብ ብሩስ ዊሊስ ባለቤት የሆነችው ኤማ ሄሚንግ ዊሊስ፣ ባለቤቷ የተጠቃበትን 'የፊት ለፊት የጭንቅላት ክፍል መጎዳት' (Frontotemporal Degeneration - FTD) የተሰኘውን የመርሳት ህመም የሚከታተል ህግ እንዲፀድቅ ሰኞ ዕለት በካሊፎርኒያ ካፒቶል ከሚገኙ ህግ አውጪዎች ጋር በመሆን ግፊት አድርጋለች።
በሴናተር ሮጀር ኒየሎ የተዘጋጀው እና ኤማ ሄሚንግ ዊሊስ ድጋፏን የሰጠችለት ይህ ረቂቅ ህግ፣ የካሊፎርኒያ የህዝብ ጤና መምሪያ ስለ FTD ህመም መረጃዎችን እንዲሰበስብ የሚያስገድድ ነው። መምሪያው በአሁኑ ወቅት የሃንቲንግተን፣ የፓርኪንሰንስ፣ የአልዛይመርስ እና የማልቲፕል ስክለሮሲስ በሽታዎችን መረጃዎች በመሰብሰብ ላይ ይገኛል። የህጉን ሂደት በተመለከተ፣ ረቂቅ ህጉ ሀምሌ 1 ቀን የህግ አውጪው ምክር ቤት የአንድ ወር የክረምት እረፍት ከመውጣቱ በፊት በምክር ቤቱ ተጠባባቂ መዝገብ ውስጥ ሰፍሮ ነበር። ምክር ቤቱ ሰኞ ዕለት ስራውን የጀመረ ሲሆን፣ ረቂቅ ህጎችን ለማጽደቅ የአንድ ወር ጊዜ ብቻ ቀርቶታል። ይህ የህግ ማዕቀፍ እስከ ጥር 1፣ 2032 ድረስ የሚራዘም ሲሆን፣ የህጉ ትንታኔ እንደሚያሳየው ለሰራተኞች እና ለኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ክፍያን ጨምሮ በዓመት 2.7 ሚሊዮን ዶላር በጀት ይጠይቃል።
ኤማ ሰኞ ዕለት በካፒቶል በሰጠችው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ እንዳብራራችው፣ FTDን በነርቭ መጎዳት በሽታዎች መዝገብ ውስጥ ማካተት የካሊፎርኒያ ታካሚዎችን መቁጠር ብቻ ሳይሆን፣ በካሊፎርኒያ የሚገኙ የባዮቴክ ተመራማሪዎች ህክምና እና ፈውስ ለማግኘት የሚፈልጉትን ጠቃሚ የመረጃ ቋት መገንባት ነው። ባለቤቷ ለመጀመሪያ ጊዜ በ2022 በበሽታው መያዙ እንደታወቀ የጠቀሰችው ኤማ፣ አሁን ላይ ህመሙን የሚያዘገይ ወይም የሚያቆም ህክምና እንደሌለ ብታምንም፣ የህመሙን መረጃዎች መሰብሰብ ግን ለምርምር ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳለው ተናግራለች። ታዋቂው ተዋናይ ስለሚገኝበት ሁኔታ ተጠይቃ ስትመልስም፣ በዚህ እጅግ ጨካኝ በሆነ በሽታ ውስጥ ሆኖ ማድረግ የሚችለውን ያህል በጥሩ ሁኔታ ላይ ይገኛል ብዬ አስባለሁ ስትል ገልጻለች።
'ፒክስ ዲዚዝ' በመባልም የሚታወቀው ይህ ህመም፣ ከግንባር ጀርባ ወይም ከጆሮ አካባቢ ባሉ የጭንቅላት ክፍሎች ላይ በሚከሰት የነርቭ ሴሎች መጎዳት የሚመጣ የጭንቅላት እክል ነው። የበሽታው ምልክቶች የባህሪ እና የስብዕና ለውጥን፣ ስሜት አልባ መሆንን ፣ ውሳኔ የመስጠት፣ የመንቀሳቀስ እና የመናገር ችግርን፣ እንዲሁም ቃላትን የመረዳት አቅም ማጣትን ያካትታሉ።
የኤፍ ቲ ዲ ማህበር የጥብቅና እና የበጎ ፈቃደኞች ተሳትፎ ዳይሬክተር የሆኑት ሜጋን ቡዝቢ እንደገለጹት፣ የታካሚ ቤተሰቦች እነዚህ ምልክቶች ሲታዩ ከሐኪሞች ግልጽ የሆነ ምላሽ ለማግኘት ብዙ ጊዜ ይቸገራሉ። ዳይሬክተሯ አክለውም፣ ይህ ሁኔታ ለብዙ የካሊፎርኒያ ቤተሰቦች የFTD ምርመራ ውጤትን ለማግኘት የሚያደርጉት ረጅም እና አድካሚ ጉዞ እውነታ መሆኑን አብራርተዋል። በአሁኑ ወቅት በሽታውን ለማከም የሚረዱ ህክምናዎች እጅግ ውስን ሲሆኑ፣ ፈውስም እስካሁን አልተገኘለትም።
የታዋቂው የፊልም ኮከብ ብሩስ ዊሊስ ባለቤት የሆነችው ኤማ ሄሚንግ ዊሊስ፣ ባለቤቷ የተጠቃበትን 'የፊት ለፊት የጭንቅላት ክፍል መጎዳት' (Frontotemporal Degeneration - FTD) የተሰኘውን የመርሳት ህመም የሚከታተል ህግ እንዲፀድቅ ሰኞ ዕለት በካሊፎርኒያ ካፒቶል ከሚገኙ ህግ አውጪዎች ጋር በመሆን ግፊት አድርጋለች።
በሴናተር ሮጀር ኒየሎ የተዘጋጀው እና ኤማ ሄሚንግ ዊሊስ ድጋፏን የሰጠችለት ይህ ረቂቅ ህግ፣ የካሊፎርኒያ የህዝብ ጤና መምሪያ ስለ FTD ህመም መረጃዎችን እንዲሰበስብ የሚያስገድድ ነው። መምሪያው በአሁኑ ወቅት የሃንቲንግተን፣ የፓርኪንሰንስ፣ የአልዛይመርስ እና የማልቲፕል ስክለሮሲስ በሽታዎችን መረጃዎች በመሰብሰብ ላይ ይገኛል። የህጉን ሂደት በተመለከተ፣ ረቂቅ ህጉ ሀምሌ 1 ቀን የህግ አውጪው ምክር ቤት የአንድ ወር የክረምት እረፍት ከመውጣቱ በፊት በምክር ቤቱ ተጠባባቂ መዝገብ ውስጥ ሰፍሮ ነበር። ምክር ቤቱ ሰኞ ዕለት ስራውን የጀመረ ሲሆን፣ ረቂቅ ህጎችን ለማጽደቅ የአንድ ወር ጊዜ ብቻ ቀርቶታል። ይህ የህግ ማዕቀፍ እስከ ጥር 1፣ 2032 ድረስ የሚራዘም ሲሆን፣ የህጉ ትንታኔ እንደሚያሳየው ለሰራተኞች እና ለኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ክፍያን ጨምሮ በዓመት 2.7 ሚሊዮን ዶላር በጀት ይጠይቃል።
ኤማ ሰኞ ዕለት በካፒቶል በሰጠችው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ እንዳብራራችው፣ FTDን በነርቭ መጎዳት በሽታዎች መዝገብ ውስጥ ማካተት የካሊፎርኒያ ታካሚዎችን መቁጠር ብቻ ሳይሆን፣ በካሊፎርኒያ የሚገኙ የባዮቴክ ተመራማሪዎች ህክምና እና ፈውስ ለማግኘት የሚፈልጉትን ጠቃሚ የመረጃ ቋት መገንባት ነው። ባለቤቷ ለመጀመሪያ ጊዜ በ2022 በበሽታው መያዙ እንደታወቀ የጠቀሰችው ኤማ፣ አሁን ላይ ህመሙን የሚያዘገይ ወይም የሚያቆም ህክምና እንደሌለ ብታምንም፣ የህመሙን መረጃዎች መሰብሰብ ግን ለምርምር ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳለው ተናግራለች። ታዋቂው ተዋናይ ስለሚገኝበት ሁኔታ ተጠይቃ ስትመልስም፣ በዚህ እጅግ ጨካኝ በሆነ በሽታ ውስጥ ሆኖ ማድረግ የሚችለውን ያህል በጥሩ ሁኔታ ላይ ይገኛል ብዬ አስባለሁ ስትል ገልጻለች።
'ፒክስ ዲዚዝ' በመባልም የሚታወቀው ይህ ህመም፣ ከግንባር ጀርባ ወይም ከጆሮ አካባቢ ባሉ የጭንቅላት ክፍሎች ላይ በሚከሰት የነርቭ ሴሎች መጎዳት የሚመጣ የጭንቅላት እክል ነው። የበሽታው ምልክቶች የባህሪ እና የስብዕና ለውጥን፣ ስሜት አልባ መሆንን ፣ ውሳኔ የመስጠት፣ የመንቀሳቀስ እና የመናገር ችግርን፣ እንዲሁም ቃላትን የመረዳት አቅም ማጣትን ያካትታሉ።
የኤፍ ቲ ዲ ማህበር የጥብቅና እና የበጎ ፈቃደኞች ተሳትፎ ዳይሬክተር የሆኑት ሜጋን ቡዝቢ እንደገለጹት፣ የታካሚ ቤተሰቦች እነዚህ ምልክቶች ሲታዩ ከሐኪሞች ግልጽ የሆነ ምላሽ ለማግኘት ብዙ ጊዜ ይቸገራሉ። ዳይሬክተሯ አክለውም፣ ይህ ሁኔታ ለብዙ የካሊፎርኒያ ቤተሰቦች የFTD ምርመራ ውጤትን ለማግኘት የሚያደርጉት ረጅም እና አድካሚ ጉዞ እውነታ መሆኑን አብራርተዋል። በአሁኑ ወቅት በሽታውን ለማከም የሚረዱ ህክምናዎች እጅግ ውስን ሲሆኑ፣ ፈውስም እስካሁን አልተገኘለትም።
3 days ago
በየዓመቱ በዓለም አቀፍ ደረጃ ከ60 ሚሊዮን በላይ ሰዎች ህይወታቸውን ያጣሉ
#ethiopia | በየዓመቱ በዓለም አቀፍ ደረጃ ከ60 ሚሊዮን በላይ ሰዎች በተለያዩ ምክንያቶች ህይወታቸውን እንደሚያጡ መረጃዎች ጠቁመዋል።
የሞት ምጣኔ በሀገራት መካከል በከፍተኛ ሁኔታ የሚለያይ ሲሆን ዋና ዋና ምክንያቶቹ የዕድሜ ስብጥር የአረጋውያን ቁጥር መብዛት ደካማ የጤና ስርዓት ጦርነትና ግጭት ዋነኞቹ ናቸው።
ከሰሀራ በታች ባሉ ሀገራት እንደ ድህነት ያሉ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጽዕኖዎች ለሞት ምጣኔው ከፍተኛ መሆን እንደምክንያትነት ይጠቀሳሉ።
በተጨማሪም በሰሃራ በታች ባሉ የአፍሪካ ሀገራት ደግሞ በቂ የህክምና አቅርቦት አለመኖር ተላላፊ በሽታዎች እና የእናቶችና ህፃናት ሞት ምጣኔ ከፍተኛ መሆን ዋና ምክንያቶች ናቸው።
በጦርነት ውስጥ ባሉ ሀገራት የሰው ህይወት ማጣት እና የጤና ተቋማት መውደም የሞት ምጣኔውን ከፍተኛ አድርጎታል።
በምስራቅ አውሮፓ እንደ ቡልጋሪያ እና ላቲቪያ ያለው የሞት ምጣኔ በቁጥር ከፍ ብሎ የሚታየው አረጋውያን በመብዛታቸው ምክንያት ነው ተብሏል።
ሔኖክ ወ/ገብርኤል
#ethiopia #getutemesgen #getunews #worldpopulation #deathrate #europe #africa
#ethiopia | በየዓመቱ በዓለም አቀፍ ደረጃ ከ60 ሚሊዮን በላይ ሰዎች በተለያዩ ምክንያቶች ህይወታቸውን እንደሚያጡ መረጃዎች ጠቁመዋል።
የሞት ምጣኔ በሀገራት መካከል በከፍተኛ ሁኔታ የሚለያይ ሲሆን ዋና ዋና ምክንያቶቹ የዕድሜ ስብጥር የአረጋውያን ቁጥር መብዛት ደካማ የጤና ስርዓት ጦርነትና ግጭት ዋነኞቹ ናቸው።
ከሰሀራ በታች ባሉ ሀገራት እንደ ድህነት ያሉ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጽዕኖዎች ለሞት ምጣኔው ከፍተኛ መሆን እንደምክንያትነት ይጠቀሳሉ።
በተጨማሪም በሰሃራ በታች ባሉ የአፍሪካ ሀገራት ደግሞ በቂ የህክምና አቅርቦት አለመኖር ተላላፊ በሽታዎች እና የእናቶችና ህፃናት ሞት ምጣኔ ከፍተኛ መሆን ዋና ምክንያቶች ናቸው።
በጦርነት ውስጥ ባሉ ሀገራት የሰው ህይወት ማጣት እና የጤና ተቋማት መውደም የሞት ምጣኔውን ከፍተኛ አድርጎታል።
በምስራቅ አውሮፓ እንደ ቡልጋሪያ እና ላቲቪያ ያለው የሞት ምጣኔ በቁጥር ከፍ ብሎ የሚታየው አረጋውያን በመብዛታቸው ምክንያት ነው ተብሏል።
ሔኖክ ወ/ገብርኤል
#ethiopia #getutemesgen #getunews #worldpopulation #deathrate #europe #africa
Sponsored by
Surafel
3 days ago
በአሜሪካ በሳይክሎስፖሪያሲስ (Cyclosporiasis) ወረርሽኝ የመጀመሪያ ሞት ተመዘገበ
#ethiopia | አሜሪካ ውስጥ በCyclospora cayetanensis ተውሳክ የሚከሰተው የሳይክሎስፖሪያሲስ (Cyclosporiasis) ወረርሽኝ ከተጀመረ በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ከዚህ በሽታ ጋር በተያያዘ ሁለት ሰዎች በሚሺጋን ግዛት መሞታቸውን የግዛቱ የጤና ባለሥልጣናት አስታውቀዋል። ይህ በአሜሪካ ታሪክ ከዚህ ወረርሽኝ ጋር በተያያዘ የተመዘገበ የመጀመሪያው የሞት ክስተት ነው።
ባለሥልጣናቱ እንደገለጹት፣ ሁለቱም ሟቾች ከዚህ ቀደም ከባድ የጤና ችግሮች የነበሯቸው ሲሆን፣ በተደጋጋሚ ተቅማጥና በውኃ እጥረት (dehydration) ምክንያት የነበራቸው ሁኔታ ተባብሶ ለሞት እንዳደረሳቸው ተገልጿል። የግል መረጃቸው አልተገለጸም።
በሚሺጋን ግዛት ብቻ እስካሁን ከ11,000 በላይ ተጠርጣሪ ወይም የተመዘገቡ ኬሶች ሲኖሩ፣ 193 ሰዎች ሆስፒታል ገብተዋል። በመላው አሜሪካ ደግሞ ከ6,700 በላይ በላብራቶሪ የተረጋገጡ ኬሶች ተመዝግበዋል፣ ተጨማሪ ብዙ ሺህ ጉዳዮችም እየተመረመሩ ይገኛሉ።
የበሽታው ምንጭ ምንድን ነው?
የአሜሪካ የበሽታ መከላከልና መቆጣጠሪያ ማዕከል (CDC) እና የምግብና መድኃኒት ባለሥልጣን (FDA) እያካሄዱት ባለው ምርመራ፣ ወረርሽኙ በዋነኝነት ከተበከለ የአይስበርግ ሰላጣ (iceberg lettuce) ጋር የተያያዘ ሊሆን እንደሚችል ተጠርጥሯል። ሆኖም ምርመራው አሁንም በመቀጠል ላይ ሲሆን የመጨረሻ ማረጋገጫ አልተሰጠም።
የበሽታው ምልክቶች
ከባድ የውኃ ተቅማጥ
የሆድ ህመም
ማቅለሽለሽ
ድካም
የምግብ ፍላጎት መቀነስ
አንዳንድ ጊዜ ትኩሳት
በጤናማ ሰዎች ላይ በአብዛኛው ሕክምና በመውሰድ ይድናል፤ ነገር ግን አረጋውያን፣ የበሽታ መከላከያ አቅማቸው ዝቅተኛ የሆኑ ሰዎች እና ሌሎች ከባድ የጤና ችግሮች ያሉባቸው ሰዎች ለከፍተኛ አደጋ ሊጋለጡ ይችላሉ።
የጤና ባለሥልጣናት የሰጡት ምክር
ጥሬ አትክልቶችንና ፍራፍሬዎችን በደንብ በማጠብ ይጠቀሙ።
የተጠረጠሩ የሰላጣ ምርቶችን አይጠቀሙ።
ተቅማጥ ከቀጠለ ወይም የውኃ እጥረት ምልክቶች ከታዩ በፍጥነት ወደ ጤና ተቋም ይሂዱ።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#ethiopia | አሜሪካ ውስጥ በCyclospora cayetanensis ተውሳክ የሚከሰተው የሳይክሎስፖሪያሲስ (Cyclosporiasis) ወረርሽኝ ከተጀመረ በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ከዚህ በሽታ ጋር በተያያዘ ሁለት ሰዎች በሚሺጋን ግዛት መሞታቸውን የግዛቱ የጤና ባለሥልጣናት አስታውቀዋል። ይህ በአሜሪካ ታሪክ ከዚህ ወረርሽኝ ጋር በተያያዘ የተመዘገበ የመጀመሪያው የሞት ክስተት ነው።
ባለሥልጣናቱ እንደገለጹት፣ ሁለቱም ሟቾች ከዚህ ቀደም ከባድ የጤና ችግሮች የነበሯቸው ሲሆን፣ በተደጋጋሚ ተቅማጥና በውኃ እጥረት (dehydration) ምክንያት የነበራቸው ሁኔታ ተባብሶ ለሞት እንዳደረሳቸው ተገልጿል። የግል መረጃቸው አልተገለጸም።
በሚሺጋን ግዛት ብቻ እስካሁን ከ11,000 በላይ ተጠርጣሪ ወይም የተመዘገቡ ኬሶች ሲኖሩ፣ 193 ሰዎች ሆስፒታል ገብተዋል። በመላው አሜሪካ ደግሞ ከ6,700 በላይ በላብራቶሪ የተረጋገጡ ኬሶች ተመዝግበዋል፣ ተጨማሪ ብዙ ሺህ ጉዳዮችም እየተመረመሩ ይገኛሉ።
የበሽታው ምንጭ ምንድን ነው?
የአሜሪካ የበሽታ መከላከልና መቆጣጠሪያ ማዕከል (CDC) እና የምግብና መድኃኒት ባለሥልጣን (FDA) እያካሄዱት ባለው ምርመራ፣ ወረርሽኙ በዋነኝነት ከተበከለ የአይስበርግ ሰላጣ (iceberg lettuce) ጋር የተያያዘ ሊሆን እንደሚችል ተጠርጥሯል። ሆኖም ምርመራው አሁንም በመቀጠል ላይ ሲሆን የመጨረሻ ማረጋገጫ አልተሰጠም።
የበሽታው ምልክቶች
ከባድ የውኃ ተቅማጥ
የሆድ ህመም
ማቅለሽለሽ
ድካም
የምግብ ፍላጎት መቀነስ
አንዳንድ ጊዜ ትኩሳት
በጤናማ ሰዎች ላይ በአብዛኛው ሕክምና በመውሰድ ይድናል፤ ነገር ግን አረጋውያን፣ የበሽታ መከላከያ አቅማቸው ዝቅተኛ የሆኑ ሰዎች እና ሌሎች ከባድ የጤና ችግሮች ያሉባቸው ሰዎች ለከፍተኛ አደጋ ሊጋለጡ ይችላሉ።
የጤና ባለሥልጣናት የሰጡት ምክር
ጥሬ አትክልቶችንና ፍራፍሬዎችን በደንብ በማጠብ ይጠቀሙ።
የተጠረጠሩ የሰላጣ ምርቶችን አይጠቀሙ።
ተቅማጥ ከቀጠለ ወይም የውኃ እጥረት ምልክቶች ከታዩ በፍጥነት ወደ ጤና ተቋም ይሂዱ።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
3 days ago
በኦቶና ሆስፒታል የላብራቶሪ መሳሪያዎችን ሊሰርቅ የነበረ የጥበቃ ሰራተኛ እጅ ከፍንጂ ተያዘ
በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ኮምፕሬሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል (ኦቶና) ሦስት ወሳኝ የላብራቶሪ ማይክሮስኮፖችን አውጥቶ ለመሰወር ሲሞክር የነበረ የጥበቃ ሰራተኛ በተረኛ ጥበቃዎች ብርቱ ክትትልና ተጋድሎ እጅ ከፍንጂ መያዙ ተገለጸ።
በትላትናው እለተ የተፈጸመው ይህ ድርጊት ተራ የሕክምና ዕቃ ስርቆት ሳይሆን፣ የሺዎችን ሕይወት እና የሆስፒታሉን ዕለታዊ የሕክምና አገልግሎት ቀጥተኛ አደጋ ላይ የጣለ ከባድ ወንጀል መሆኑን ባለሙያዎች ይናገራሉ።
ተጠርጣሪው ግለሰብ የሕክምና መገልገያዎቹን ደብቆ ከሆስፒታሉ ግቢ ሊያወጣ ሲል በተረኛ ባልደረቦቹ ንቁ ክትትል በቁጥጥር ስር ውሏል። ድርጊቱ በግለሰቡ ብቻ የተፈጸመ ሳይሆን በጀርባ ያሉ አመቻቾችና አቀናባሪዎች እንዳሉበት በመጠረጠሩ፣ ወንጀሉን ያስተባበሩ አካላት በሙሉ ተለይተው ተገቢው የሕግ ትርጉም እንዲሰጣቸውና አስተማሪ ቅጣት እንዲያገኙ ጉዳዩ በትኩረት እየተከታተለ ይገኛል።
በአንድ አጠቃላይ ሆስፒታል ውስጥ ማይክሮስኮፕ ማለት የተደበቁ በሽታዎችን አውጥቶ በማሳየት የሕሙማንን ሕይወት የሚያስጥል ዋና መመርመሪያ መሳሪያ ነው።
እነዚህን መገልገያዎች ማጣት በሕሙማን ላይ የሚከተሉትን ከባድ የጤና አደጋዎች ያስከትላል፦
እንደ ወባ፣ ቲቢ እና የተለያዩ ከባድ የባክቴሪያ ኢንፌክሽኖችን በፍጥነት በመመርመር አስቸኳይ የሕክምና ውሳኔ ለመስጠት ያገለግላሉ።
የደም ማነስን (Anemia) እና የደም ካንሰርን (Leukemia) በጥንቃቄ ለይቶ ለማወቅ ወሳኝ መገልገያዎች ናቸው።
እነዚህ መሳሪያዎች ከአገልግሎት ውጭ ሲሆኑ የላብራቶሪ ውጤቶች ይዘገያሉ፤ ይህም በተለይ በፅኑ ሕሙማን፣ በሕፃናትና ነፍሰ ጡራት ሕይወት ላይ የቀጥታ አደጋ ይደቅናል።
የሕዝብና የመንግሥት ሀብት የሆኑትን የሕክምና መገልገያዎች ከስርቆትና ከእጅ አዙር ሴራ መጠበቅ የሁላችንም ኃላፊነት ነው።
በሆስፒታሉ ግቢ ውስጥ የታየው የተረኛ ጥበቃዎች ንቅናቄ የሚደነቅ ሲሆን፣ የወንጀሉ ተሳታፊዎች በሙሉ ለሕግ እንዲቀርቡ የጀመረው ክትትል ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል።
Via ጉርሻ page
በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ኮምፕሬሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል (ኦቶና) ሦስት ወሳኝ የላብራቶሪ ማይክሮስኮፖችን አውጥቶ ለመሰወር ሲሞክር የነበረ የጥበቃ ሰራተኛ በተረኛ ጥበቃዎች ብርቱ ክትትልና ተጋድሎ እጅ ከፍንጂ መያዙ ተገለጸ።
በትላትናው እለተ የተፈጸመው ይህ ድርጊት ተራ የሕክምና ዕቃ ስርቆት ሳይሆን፣ የሺዎችን ሕይወት እና የሆስፒታሉን ዕለታዊ የሕክምና አገልግሎት ቀጥተኛ አደጋ ላይ የጣለ ከባድ ወንጀል መሆኑን ባለሙያዎች ይናገራሉ።
ተጠርጣሪው ግለሰብ የሕክምና መገልገያዎቹን ደብቆ ከሆስፒታሉ ግቢ ሊያወጣ ሲል በተረኛ ባልደረቦቹ ንቁ ክትትል በቁጥጥር ስር ውሏል። ድርጊቱ በግለሰቡ ብቻ የተፈጸመ ሳይሆን በጀርባ ያሉ አመቻቾችና አቀናባሪዎች እንዳሉበት በመጠረጠሩ፣ ወንጀሉን ያስተባበሩ አካላት በሙሉ ተለይተው ተገቢው የሕግ ትርጉም እንዲሰጣቸውና አስተማሪ ቅጣት እንዲያገኙ ጉዳዩ በትኩረት እየተከታተለ ይገኛል።
በአንድ አጠቃላይ ሆስፒታል ውስጥ ማይክሮስኮፕ ማለት የተደበቁ በሽታዎችን አውጥቶ በማሳየት የሕሙማንን ሕይወት የሚያስጥል ዋና መመርመሪያ መሳሪያ ነው።
እነዚህን መገልገያዎች ማጣት በሕሙማን ላይ የሚከተሉትን ከባድ የጤና አደጋዎች ያስከትላል፦
እንደ ወባ፣ ቲቢ እና የተለያዩ ከባድ የባክቴሪያ ኢንፌክሽኖችን በፍጥነት በመመርመር አስቸኳይ የሕክምና ውሳኔ ለመስጠት ያገለግላሉ።
የደም ማነስን (Anemia) እና የደም ካንሰርን (Leukemia) በጥንቃቄ ለይቶ ለማወቅ ወሳኝ መገልገያዎች ናቸው።
እነዚህ መሳሪያዎች ከአገልግሎት ውጭ ሲሆኑ የላብራቶሪ ውጤቶች ይዘገያሉ፤ ይህም በተለይ በፅኑ ሕሙማን፣ በሕፃናትና ነፍሰ ጡራት ሕይወት ላይ የቀጥታ አደጋ ይደቅናል።
የሕዝብና የመንግሥት ሀብት የሆኑትን የሕክምና መገልገያዎች ከስርቆትና ከእጅ አዙር ሴራ መጠበቅ የሁላችንም ኃላፊነት ነው።
በሆስፒታሉ ግቢ ውስጥ የታየው የተረኛ ጥበቃዎች ንቅናቄ የሚደነቅ ሲሆን፣ የወንጀሉ ተሳታፊዎች በሙሉ ለሕግ እንዲቀርቡ የጀመረው ክትትል ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል።
Via ጉርሻ page
5 days ago
«ከለውጡ በኋላ የነበረውን የመታፈን ስሜት ለማናፈስ በተደረገው ጥረት ውስጥ የተቀላቀሉ ቢምቢዎች ነበሩ»- ጠ/ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የ2010 ዓ.ም. የለውጥ ጉዞንና ከዚያ በኋላ በሀገሪቱ የፖለቲካ ምህዳር ውስጥ የታዩትን ኩነቶች አስመልክተው ከአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን ጋር ባደረጉት ቆይታ በሰጡት ማብራሪያ፣ የዐማራ ሕዝብ እንደማንኛውም የኢትዮጵያ ሕዝብ ለለውጥና ለዕድገት ከፍተኛ ተጋድሎ ማድረጉን ገልጸዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ እንደገለጹት፣ ከለውጡ ማግሥት የነበረው ጉዞ መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ በከፍተኛ ተስፋ የተሞላበት፣ «በዚህ ለውጥ እሠራለሁ፣ አተርፋለሁ፣ ሀገር አጠናለሁ» የሚል ሕልም በሰፊው የተገለጸበት ወቅት ነበር። ከለውጡ በፊት በነበረው የፖለቲካና የኢኮኖሚ ሥርዓት ውስጥ የመዘጋትና የመታፈን ምልክቶች እንደነበሩ የጠቆሙት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ የተዘጋን ቤት መስኮት ከፍቶ እንደማናፈስ ሁሉ ፖለቲካውንም ማናፈስ አስፈላጊ ነበር ብለዋል።
ሆኖም መስኮቶች ሲከፈቱ ንጹሕ አየር ብቻ ሳይሆን «ቢምቢዎችና ትንኞችም» አብረው እንደሚገቡ በመግለጽ፣ በፖለቲካው ምህዳር መከፈት ምክንያት አጋጣሚውን በመጠቀም ሁኔታዎችን ወደ ሥጋትና ድንግዝግዝነት ለመቀየር የሞከሩ አካላት እንደነበሩ አስረድተዋል።
«ቢምቢ በሳይዟ በጣም ትንሽ ናት፤ ነገር ግን ድምፅ በማሰማት እንዳትተኛ ታውክሃለች። ሁለተኛውና ከዚያ የሚከፋው ደግሞ በመንደፍ ደምን መምጠጧና በሽታ ማምጣቷ ነው። በኢትዮጵያ ፖለቲካ ዓውድ ውስጥም ከፍተኛ ድምፅ በማሰማት ለማወክ የሚሞክሩ፣ የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ለማደናቀፍና ህልውናዋን ለመገዳደር ከሚፈልጉ ኃይሎች ጋር እስከመሰለፍ የሄዱ አካላት ነበሩ።»
በወቅቱ በተፈጠሩት ነገሮች ምክንያት በሕዝቡ ዘንድ ምንድን ነው የመጣብን ሥጋት ተፈጥሮ የነበረ ቢሆንም፣ ነገሮች እያዋሉ እያደሩ ሲመጡ ግን የ«መደመር» መንገድ ብቸኛው አማራጭ መሆኑንና ለመበልጸግ የሚደረገው ጥረት ተገቢ መሆኑን ሕዝቡ ማመኑን ገልጸዋል።
በመጨረሻም፣ ሕዝቡ ይህንን እምነቱን በምርጫ ማረጋገጡን የጠቆሙት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ብቸኛው ኢትዮጵያን የማጽኛ መንገድ ታሪካዊውን ውህደትና እህትነት በሚያርቅ፣ በሚያድስና በሚያሰፋ መንገድ መሄድ፣ ተከባብሮና ተዋዶ በጋራ በመስራት ሀገርን ማጽናት ብቻ መሆኑን አብራርተዋል።
Seledadotio
Seledadotio
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የ2010 ዓ.ም. የለውጥ ጉዞንና ከዚያ በኋላ በሀገሪቱ የፖለቲካ ምህዳር ውስጥ የታዩትን ኩነቶች አስመልክተው ከአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን ጋር ባደረጉት ቆይታ በሰጡት ማብራሪያ፣ የዐማራ ሕዝብ እንደማንኛውም የኢትዮጵያ ሕዝብ ለለውጥና ለዕድገት ከፍተኛ ተጋድሎ ማድረጉን ገልጸዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ እንደገለጹት፣ ከለውጡ ማግሥት የነበረው ጉዞ መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ በከፍተኛ ተስፋ የተሞላበት፣ «በዚህ ለውጥ እሠራለሁ፣ አተርፋለሁ፣ ሀገር አጠናለሁ» የሚል ሕልም በሰፊው የተገለጸበት ወቅት ነበር። ከለውጡ በፊት በነበረው የፖለቲካና የኢኮኖሚ ሥርዓት ውስጥ የመዘጋትና የመታፈን ምልክቶች እንደነበሩ የጠቆሙት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ የተዘጋን ቤት መስኮት ከፍቶ እንደማናፈስ ሁሉ ፖለቲካውንም ማናፈስ አስፈላጊ ነበር ብለዋል።
ሆኖም መስኮቶች ሲከፈቱ ንጹሕ አየር ብቻ ሳይሆን «ቢምቢዎችና ትንኞችም» አብረው እንደሚገቡ በመግለጽ፣ በፖለቲካው ምህዳር መከፈት ምክንያት አጋጣሚውን በመጠቀም ሁኔታዎችን ወደ ሥጋትና ድንግዝግዝነት ለመቀየር የሞከሩ አካላት እንደነበሩ አስረድተዋል።
«ቢምቢ በሳይዟ በጣም ትንሽ ናት፤ ነገር ግን ድምፅ በማሰማት እንዳትተኛ ታውክሃለች። ሁለተኛውና ከዚያ የሚከፋው ደግሞ በመንደፍ ደምን መምጠጧና በሽታ ማምጣቷ ነው። በኢትዮጵያ ፖለቲካ ዓውድ ውስጥም ከፍተኛ ድምፅ በማሰማት ለማወክ የሚሞክሩ፣ የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ለማደናቀፍና ህልውናዋን ለመገዳደር ከሚፈልጉ ኃይሎች ጋር እስከመሰለፍ የሄዱ አካላት ነበሩ።»
በወቅቱ በተፈጠሩት ነገሮች ምክንያት በሕዝቡ ዘንድ ምንድን ነው የመጣብን ሥጋት ተፈጥሮ የነበረ ቢሆንም፣ ነገሮች እያዋሉ እያደሩ ሲመጡ ግን የ«መደመር» መንገድ ብቸኛው አማራጭ መሆኑንና ለመበልጸግ የሚደረገው ጥረት ተገቢ መሆኑን ሕዝቡ ማመኑን ገልጸዋል።
በመጨረሻም፣ ሕዝቡ ይህንን እምነቱን በምርጫ ማረጋገጡን የጠቆሙት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ብቸኛው ኢትዮጵያን የማጽኛ መንገድ ታሪካዊውን ውህደትና እህትነት በሚያርቅ፣ በሚያድስና በሚያሰፋ መንገድ መሄድ፣ ተከባብሮና ተዋዶ በጋራ በመስራት ሀገርን ማጽናት ብቻ መሆኑን አብራርተዋል።
Seledadotio
Seledadotio
6 days ago
"ደህና ነኝ!" ሊመረቅ ነው!
የጋዜጠኛና መምህር ዐቢይ ይልማ 5ኛ “ደህና ነኝ - እግዚአብሔር ይመስገን” የተሰኘ መንፈ-ሳይንሳዊ መፅሐፍ የፊታችን ነሐሴ 2/2018 ዓም ፣ ቅዳሜ ጠዋት 4፡00 ቦሌ በሚገኘው ዓለም ሲኒማ ይመረቃል፡፡
መፅሐፉ አሁን በትውልዱም ፣ በሐገራችንም የገባውን የጭንቀት ፣ የፍርሃት ፣ የባዶነት ስሜት ፣ የተስፋ መቁረጥ ፣ የካንሰር ፣ የስኳር ፣ ስትሮክና መሰል በሽታዎች ጥቃትን በዕውቀት ያክማል፡፡ በራስ ኩነኔ ፣ በሱሰኝነት ፣ በገንዘብ እጦት ወዘተ (ብቻ) ሕይወትም ኑሮም ለከበዳት ነፍስ አስገራሚ ምስጢራትን ይበታትናል፡፡ ፀሐፊው ዐቢይ ይልማ በሕይወቱ ፣ በመኖርና መሞት መካከል ከተፋለመባቸው የ12 ዓመታት የሕይወት ጦርነት አሸናፊነት ውስጥ “ደህና ነኝ ፤ እግዚአብሔር ይመስገን!” መጽሐፍ ተወልዳለች።
በምረቃው ዕለት ታላላቅ እንግዶች የሚታደሙ ሲሆን መርሀ ግብሩንም የሚያዋዙ የጥበብ መሰናዶዎችም እንደሚኖሩ ከኮሚቴው ያገኘነው መረጃ ያስረዳል።
የጋዜጠኛና መምህር ዐቢይ ይልማ 5ኛ “ደህና ነኝ - እግዚአብሔር ይመስገን” የተሰኘ መንፈ-ሳይንሳዊ መፅሐፍ የፊታችን ነሐሴ 2/2018 ዓም ፣ ቅዳሜ ጠዋት 4፡00 ቦሌ በሚገኘው ዓለም ሲኒማ ይመረቃል፡፡
መፅሐፉ አሁን በትውልዱም ፣ በሐገራችንም የገባውን የጭንቀት ፣ የፍርሃት ፣ የባዶነት ስሜት ፣ የተስፋ መቁረጥ ፣ የካንሰር ፣ የስኳር ፣ ስትሮክና መሰል በሽታዎች ጥቃትን በዕውቀት ያክማል፡፡ በራስ ኩነኔ ፣ በሱሰኝነት ፣ በገንዘብ እጦት ወዘተ (ብቻ) ሕይወትም ኑሮም ለከበዳት ነፍስ አስገራሚ ምስጢራትን ይበታትናል፡፡ ፀሐፊው ዐቢይ ይልማ በሕይወቱ ፣ በመኖርና መሞት መካከል ከተፋለመባቸው የ12 ዓመታት የሕይወት ጦርነት አሸናፊነት ውስጥ “ደህና ነኝ ፤ እግዚአብሔር ይመስገን!” መጽሐፍ ተወልዳለች።
በምረቃው ዕለት ታላላቅ እንግዶች የሚታደሙ ሲሆን መርሀ ግብሩንም የሚያዋዙ የጥበብ መሰናዶዎችም እንደሚኖሩ ከኮሚቴው ያገኘነው መረጃ ያስረዳል።
7 days ago
የአየር ንብረት ለውጥ አውሮፓን እያመሰ ነው
* በከፍተኛ ሙቀት እና በሰደድ እሳት ሺዎች ሕይወታቸውን አጥተዋል
#ethiopia | የአየር ንብረት ለውጥ በአውሮፓ ከፍተኛ ሰብዓዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ሥነ-ምህዳራዊ ቀውስ እያስከተለ መሆኑን የቅርብ ጊዜ ዓለም አቀፍ መረጃዎች ያመለክታሉ።
በሰኔ መጨረሻ እና በሐምሌ ወር የተከሰቱ ከባድ የሙቀት ማዕበሎች በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎችን ለሕልፈት ዳርገዋል፤ በበርካታ አገራት ደግሞ ሰደድ እሳቶች መኖሪያ ቤቶችን፣ ደኖችንና የግብርና መሬቶችን አውድመዋል።
የአውሮፓ በሽታ መከላከያ ማዕከል (ECDC) እና የዓለም ጤና ድርጅት (WHO) በሚደግፉት የEuroMOMO የሞት ክትትል መረጃ መሠረት፣ በሰኔ 22 እስከ 28 ቀን 2026 ብቻ ከ10 ሺህ በላይ ተጨማሪ ሞቶች ተመዝግበዋል።
ከእነዚህ ውስጥ ከ9 ሺህ በላይ የሚሆኑት ዕድሜያቸው 65 ዓመት እና ከዚያ በላይ የሆኑ ሰዎች ናቸው። ባለሙያዎች ይህን ያልተለመደ የሞት ጭማሪ በዋነኝነት ከከፍተኛ ሙቀት ጋር ያያይዙታል።
በጀርመን ብቻ በ2026 እስከ ሐምሌ መጨረሻ ድረስ 9,800 የሚጠጉ ከሙቀት ጋር የተያያዙ ሞቶች መመዝገባቸው ተገልጿል።
በእንግሊዝ ደግሞ 2,800 በላይ ሰዎች በሙቀት ምክንያት መሞታቸው ተነግሯል፤ ይህም የ2022 ሪከርድን ሊበልጥ እንደሚችል ባለሥልጣናት አስጠንቅቀዋል።
በፈረንሳይ፣ ስፔን፣ ግሪክ፣ ጣሊያን እና ፖርቱጋል የተቀሰቀሱ ሰደድ እሳቶች በመቶ ሺዎች ሄክታር የሚቆጠር ደን እንዲቃጠል አድርገዋል።
በፈረንሳይ ብቻ ከ220 ሺህ በላይ ሰዎች ከመኖሪያ ቀያቸው ተፈናቅለዋል፤ በግሪክ ደግሞ ሶስት የአደጋ አደራሽ ሠራተኞች በእሳት ማጥፋት ስራ ላይ ሕይወታቸውን አጥተዋል።
ሳይንቲስቶች እንደሚገልጹት፣ በሰኔ መጨረሻ የተመዘገበው የሙቀት ማዕበል የሰው ልጅ የፈጠረው የአየር ንብረት ለውጥ ባይኖር ሊከሰት ፈጽሞ የማይችል ነበር።
አውሮፓ በዓለም ላይ ከሌሎች አህጉራት በበለጠ ፍጥነት እየሞቀች ያለች አህጉር መሆኗም ችግሩን እያባባሰው ነው።
በዚህ ሁኔታ የአውሮፓ መንግሥታት የሙቀት አደጋ ማስጠንቀቂያ ሥርዓቶችን ማጠናከር፣ ለአረጋውያንና ለተጋላጭ ማኅበረሰቦች የጤና ጥበቃን ማሳደግ፣ እንዲሁም የካርቦን ልቀትን ለመቀነስ የበለጠ ቁርጠኛ እርምጃ እንዲወስዱ ተጠይቀዋል።
በሌላ በኩል፣ ኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም በ"አረንጓዴ ዐሻራ" መርሃ ግብር ባለፉት ሰባት ዓመታት ከ48 ቢሊዮን በላይ ችግኞችን በመትከል የደን ሽፋኗን ለማሳደግና የአየር ንብረት ለውጥን ለመቀነስ ጥረት እያደረገች ትገኛለች።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
* በከፍተኛ ሙቀት እና በሰደድ እሳት ሺዎች ሕይወታቸውን አጥተዋል
#ethiopia | የአየር ንብረት ለውጥ በአውሮፓ ከፍተኛ ሰብዓዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ሥነ-ምህዳራዊ ቀውስ እያስከተለ መሆኑን የቅርብ ጊዜ ዓለም አቀፍ መረጃዎች ያመለክታሉ።
በሰኔ መጨረሻ እና በሐምሌ ወር የተከሰቱ ከባድ የሙቀት ማዕበሎች በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎችን ለሕልፈት ዳርገዋል፤ በበርካታ አገራት ደግሞ ሰደድ እሳቶች መኖሪያ ቤቶችን፣ ደኖችንና የግብርና መሬቶችን አውድመዋል።
የአውሮፓ በሽታ መከላከያ ማዕከል (ECDC) እና የዓለም ጤና ድርጅት (WHO) በሚደግፉት የEuroMOMO የሞት ክትትል መረጃ መሠረት፣ በሰኔ 22 እስከ 28 ቀን 2026 ብቻ ከ10 ሺህ በላይ ተጨማሪ ሞቶች ተመዝግበዋል።
ከእነዚህ ውስጥ ከ9 ሺህ በላይ የሚሆኑት ዕድሜያቸው 65 ዓመት እና ከዚያ በላይ የሆኑ ሰዎች ናቸው። ባለሙያዎች ይህን ያልተለመደ የሞት ጭማሪ በዋነኝነት ከከፍተኛ ሙቀት ጋር ያያይዙታል።
በጀርመን ብቻ በ2026 እስከ ሐምሌ መጨረሻ ድረስ 9,800 የሚጠጉ ከሙቀት ጋር የተያያዙ ሞቶች መመዝገባቸው ተገልጿል።
በእንግሊዝ ደግሞ 2,800 በላይ ሰዎች በሙቀት ምክንያት መሞታቸው ተነግሯል፤ ይህም የ2022 ሪከርድን ሊበልጥ እንደሚችል ባለሥልጣናት አስጠንቅቀዋል።
በፈረንሳይ፣ ስፔን፣ ግሪክ፣ ጣሊያን እና ፖርቱጋል የተቀሰቀሱ ሰደድ እሳቶች በመቶ ሺዎች ሄክታር የሚቆጠር ደን እንዲቃጠል አድርገዋል።
በፈረንሳይ ብቻ ከ220 ሺህ በላይ ሰዎች ከመኖሪያ ቀያቸው ተፈናቅለዋል፤ በግሪክ ደግሞ ሶስት የአደጋ አደራሽ ሠራተኞች በእሳት ማጥፋት ስራ ላይ ሕይወታቸውን አጥተዋል።
ሳይንቲስቶች እንደሚገልጹት፣ በሰኔ መጨረሻ የተመዘገበው የሙቀት ማዕበል የሰው ልጅ የፈጠረው የአየር ንብረት ለውጥ ባይኖር ሊከሰት ፈጽሞ የማይችል ነበር።
አውሮፓ በዓለም ላይ ከሌሎች አህጉራት በበለጠ ፍጥነት እየሞቀች ያለች አህጉር መሆኗም ችግሩን እያባባሰው ነው።
በዚህ ሁኔታ የአውሮፓ መንግሥታት የሙቀት አደጋ ማስጠንቀቂያ ሥርዓቶችን ማጠናከር፣ ለአረጋውያንና ለተጋላጭ ማኅበረሰቦች የጤና ጥበቃን ማሳደግ፣ እንዲሁም የካርቦን ልቀትን ለመቀነስ የበለጠ ቁርጠኛ እርምጃ እንዲወስዱ ተጠይቀዋል።
በሌላ በኩል፣ ኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም በ"አረንጓዴ ዐሻራ" መርሃ ግብር ባለፉት ሰባት ዓመታት ከ48 ቢሊዮን በላይ ችግኞችን በመትከል የደን ሽፋኗን ለማሳደግና የአየር ንብረት ለውጥን ለመቀነስ ጥረት እያደረገች ትገኛለች።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
8 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የቀድሞው የአሜሪካ ከፍተኛ የኢንፌክሽን በሽታዎች ኤክስፐርት ዶክተር አንቶኒ ፋውቺ፣ ረቡዕ ዕለት በሴኔት ሀገር ውስጥ ደኅንነት ኮሚቴ ፊት ቀርበው ከኮሚቴው ሰብሳቢ ሪፐብሊካኑ ሴናተር ራንድ ፖል ጋር የከረረ ፍጥጫ ውስጥ ገብተዋል። ዶክተር ፋውቺ በችሎቱ ላይ የቀረቡት በሴናተር ፖል መጥሪያ አዛዥነት ሲሆን፣ ውጥረት በነገሰበት በዚህ ችሎት ላይ ማንኛውንም ጥያቄ ላለመመለስ አምስተኛውን የሕገ-መንግስት ማሻሻያ መብታቸውን እንደሚጠቀሙ ይፋ አድርገዋል።
ዶክተር ፋውቺ በመክፈቻ ንግግራቸው፣ ሴናተር ራንድ ፖል በቅርቡ የግል ማስታወሻ ደብተራቸውን ይፋ ማድረጋቸውን በመኮነን ጥብቅ መግለጫ ሰጥተዋል። "ሴናተር ፖል እኔን ለፍርድ ለማቅረብ ካለው ግልጽ እብደት፣ ስለ እኔ ከተናገራቸው ስም አጥፊ ንግግሮች እና እኔን ለማሳፈርና ለማስፈራራት ሲል ይፋ ካደረገው የግል ማስታወሻ ደብተሬ በመነሳት፤ እኔ ልደርስበት የምችለው አንድ መደምደሚያ ብቻ ነው። እሱ እኔን ወደዚህ ኮሚቴ የጠራበት ብቸኛ ምክንያት እስር ቤት እንድገባ የገባውን ቃል የሚያረጋግጥልኝን ማንኛውንም ቃል ከእኔ አፍ ለማውጣት ነው" ብለዋል። አክለውም በህግ አማካሪዎቻቸው ምክር መሰረት ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች በሙሉ ምላሽ ከመስጠት እንደሚቆጠቡ አስታውቀዋል።
በችሎቱ ወቅት ሴናተር ራንድ ፖል እና ሌሎች ሪፐብሊካን ሴናተሮች በቻይና ውሃን ላቦራቶሪ ስለተደረገው የቫይረስ ምርምር፣ ስለ ኮቪድ-19 ክትባቶች እና በፕሬዝዳንት ጆ ባይደን ስለተሰጣቸው የፕሬዝዳንታዊ ምህረት ተደጋጋሚ ጥያቄዎችን ቢያቀርቡም፣ ዶክተር ፋውቺ "በጠበቃዬ ምክር መሰረት በአምስተኛው ማሻሻያ መብቴ በመጠቀም ምላሽ ከመስጠት እቆጠባለሁ" የሚለውን አቋማቸውን አልቀየሩም።
በችሎቱ መሀል ድባቡ ይበልጥ የከረረው ሴናተር ራንድ ፖል የዶክተር ፋውቺን ጠበቃ "ያለ ፈቃድ ተናግረሃል" በሚል ከችሎት ክፍሉ በደኅንነት አባላት አስወጥተው እንዲባረሩ ሲያደርጉ ነው። ይህንን ተከትሎ የፋውቺ ጠበቃ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ ደንበኛቸው ህገ-መንግስታዊ መብታቸውን የመጠቀም ሙሉ ህጋዊ መብት እንዳላቸው ተናግረዋል።
ሴናተር ራንድ ፖል፣ ዶክተር ፋውቺ ከቀድሞው ፕሬዝዳንት ባይደን ሙሉ የፕሬዝዳንት ምህረት የተሰጣቸው በመሆኑ ይህንን የምስክርነት መብት የመቃወም መብት የላቸውም ሲሉ ሞግተዋል። ፋውቺ ጥያቄዎችን ባለመመለሳቸው ምክንያት ኮሚቴው በሚቀጥለው ሳምንት በዶክተር ፋውቺ ላይ "የኮንግረስ ንቀት" ውሳኔ ለማስተላለፍ ድምፅ እንደሚሰጥ አስታውቀዋል።
በሌላ በኩል በኮሚቴው ውስጥ የሚገኙት የዴሞክራቲክ ፓርቲ አባላት እና የኮሚቴው ከፍተኛ አባል ሴናተር ጋሪ ፒተርስ፣ ሴናተር ፖል የምርጫ እና የፖለቲካ አጀንዳቸውን ለማስፈጸም ያለፈውን ታሪክ እየቆፈሩ የምርመራ ሂደቱን ለፓርቲ ጥቅም እያዋሉት ነው ሲሉ አጥብቀው ተችተዋል።
ለሶስት ሰዓታት የቆየውን ይህንን ችሎት ያጠናቀቁት ሴናተር ራንድ ፖል "ዛሬ የፋውቺ የ40 ዓመት የቁጥጥር እና የስልጣን አጠቃቀም ማጠቃለያ ነው" ካሉ በኋላ፣ የፋውቺ ውሳኔዎች በሰው ልጅ ታሪክ ውስጥ ትልቁ ሰው ሰራሽ ወረርሽኝ እንዲከሰት ምክንያት ሆነው እንደሆነ አሁንም በህሊናቸው ሊጠየቁ እንደሚገባ ተናግረዋል።
ዶክተር ፋውቺ በመክፈቻ ንግግራቸው፣ ሴናተር ራንድ ፖል በቅርቡ የግል ማስታወሻ ደብተራቸውን ይፋ ማድረጋቸውን በመኮነን ጥብቅ መግለጫ ሰጥተዋል። "ሴናተር ፖል እኔን ለፍርድ ለማቅረብ ካለው ግልጽ እብደት፣ ስለ እኔ ከተናገራቸው ስም አጥፊ ንግግሮች እና እኔን ለማሳፈርና ለማስፈራራት ሲል ይፋ ካደረገው የግል ማስታወሻ ደብተሬ በመነሳት፤ እኔ ልደርስበት የምችለው አንድ መደምደሚያ ብቻ ነው። እሱ እኔን ወደዚህ ኮሚቴ የጠራበት ብቸኛ ምክንያት እስር ቤት እንድገባ የገባውን ቃል የሚያረጋግጥልኝን ማንኛውንም ቃል ከእኔ አፍ ለማውጣት ነው" ብለዋል። አክለውም በህግ አማካሪዎቻቸው ምክር መሰረት ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች በሙሉ ምላሽ ከመስጠት እንደሚቆጠቡ አስታውቀዋል።
በችሎቱ ወቅት ሴናተር ራንድ ፖል እና ሌሎች ሪፐብሊካን ሴናተሮች በቻይና ውሃን ላቦራቶሪ ስለተደረገው የቫይረስ ምርምር፣ ስለ ኮቪድ-19 ክትባቶች እና በፕሬዝዳንት ጆ ባይደን ስለተሰጣቸው የፕሬዝዳንታዊ ምህረት ተደጋጋሚ ጥያቄዎችን ቢያቀርቡም፣ ዶክተር ፋውቺ "በጠበቃዬ ምክር መሰረት በአምስተኛው ማሻሻያ መብቴ በመጠቀም ምላሽ ከመስጠት እቆጠባለሁ" የሚለውን አቋማቸውን አልቀየሩም።
በችሎቱ መሀል ድባቡ ይበልጥ የከረረው ሴናተር ራንድ ፖል የዶክተር ፋውቺን ጠበቃ "ያለ ፈቃድ ተናግረሃል" በሚል ከችሎት ክፍሉ በደኅንነት አባላት አስወጥተው እንዲባረሩ ሲያደርጉ ነው። ይህንን ተከትሎ የፋውቺ ጠበቃ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ ደንበኛቸው ህገ-መንግስታዊ መብታቸውን የመጠቀም ሙሉ ህጋዊ መብት እንዳላቸው ተናግረዋል።
ሴናተር ራንድ ፖል፣ ዶክተር ፋውቺ ከቀድሞው ፕሬዝዳንት ባይደን ሙሉ የፕሬዝዳንት ምህረት የተሰጣቸው በመሆኑ ይህንን የምስክርነት መብት የመቃወም መብት የላቸውም ሲሉ ሞግተዋል። ፋውቺ ጥያቄዎችን ባለመመለሳቸው ምክንያት ኮሚቴው በሚቀጥለው ሳምንት በዶክተር ፋውቺ ላይ "የኮንግረስ ንቀት" ውሳኔ ለማስተላለፍ ድምፅ እንደሚሰጥ አስታውቀዋል።
በሌላ በኩል በኮሚቴው ውስጥ የሚገኙት የዴሞክራቲክ ፓርቲ አባላት እና የኮሚቴው ከፍተኛ አባል ሴናተር ጋሪ ፒተርስ፣ ሴናተር ፖል የምርጫ እና የፖለቲካ አጀንዳቸውን ለማስፈጸም ያለፈውን ታሪክ እየቆፈሩ የምርመራ ሂደቱን ለፓርቲ ጥቅም እያዋሉት ነው ሲሉ አጥብቀው ተችተዋል።
ለሶስት ሰዓታት የቆየውን ይህንን ችሎት ያጠናቀቁት ሴናተር ራንድ ፖል "ዛሬ የፋውቺ የ40 ዓመት የቁጥጥር እና የስልጣን አጠቃቀም ማጠቃለያ ነው" ካሉ በኋላ፣ የፋውቺ ውሳኔዎች በሰው ልጅ ታሪክ ውስጥ ትልቁ ሰው ሰራሽ ወረርሽኝ እንዲከሰት ምክንያት ሆነው እንደሆነ አሁንም በህሊናቸው ሊጠየቁ እንደሚገባ ተናግረዋል።
8 days ago
ብቸኝነት ያለባቸው ሰዎች ለከባድ የልብ በሽታ የመጋለጥ ዕድላቸው በ19 በመቶ እንደሚጨምር በአዲስ ጥናት ተመላከተ
ብቸኝነት የአእምሮ ጤና ጉዳይ ብቻ ሳይሆን፤ የልብን መዋቅር በቀጥታ በመጉዳት ለከፋ የጤና ችግር የሚያጋልጥ አሳሳቢ ችግር መሆኑን በአሜሪካ የልብ ማህበር (AHA) ይፋ የተደረገ አንድ አዲስ ጥናት አመላክቷል።
ጥናቱ እንዳመለከተው፣ ብቸኝነት የሰውነትን የጭንቀት መጠንን በመጨመር የጭንቀት ሆርሞኖች (እንደ ኮርቲሶል ያሉ) በሰውነታችን ውስጥ እንዲጨምሩ ያደርጋል።
ይህ ከብቸኝነት የሚመነጭ ስነ-ልቦናዊ እና ማህበራዊ ጭንቀት ደግሞ፣ በጊዜ ሂደት የልብ ቫልቭን (Heart Valve) በመጉዳት ለከፋ የልብ ጤና መቃወስ እንደሚያጋልጥ በካሊፎርኒያ ዩኒቨርሲቲ የተመራው ይህ የጥናት ቡድንአረጋግጧል።
በካሊፎርኒያ ዩኒቨርሲቲ ሀኪም የሆኑት ዶክተር ክሪስታል ዋይሊ ሴኔ እንዳሉት፤ “የህክምና ባለሙያዎች ታካሚዎቻቸውን ስለ ማህበራዊ ግንኙነቶቻቸው ሊጠይቋቸው ይገባል፤ ይህን አለማድረግ ታካሚዎችን ለከፋ የልብ ጤና እክል አልፎ ተርፎም ለሞት ሊያጋልጣቸው ይችላል" ሲሉ አስጠንቅቀዋል።
በተጨማሪም ብቸኛ የሆኑ ሰዎች ሲጋራ ማጨስን፣ ከመጠን በላይ አልኮል መጠጣትን እና የአካል ብቃት እንቅስቃሴ አለማድረግን የመሳሰሉ ጤናማ ያልሆኑ የአኗኗር ዘይቤዎችን በብዛት ስለሚከተሉ፣ ይህ ልምምድ ለልብ እና የደም ስር ጉዳት መፋጠን ተጨማሪ ምክንያት መሆኑ ተጠቁሟል።
የአሜሪካ ዋና የቀዶ ጥገና ሀኪም በፈረጆቹ 2023 ብቸኝነትን "የህዝብ ጤና ወረርሽኝ" ሲሉ ያወጁት ሲሆን፤ ችግሩ ያለዕድሜ የመሞት አደጋን በ26 በመቶ ከፍ እንደሚያደርገውና ይህም በቀን 15 ሲጋራዎችን ከማጨስ ጋር እኩል የሚመዘን ጉዳት እንዳለው መግለጻቸው ይታወሳል።
ይህ የችግሩ አሳሳቢነት የዓለም ጤና ድርጅት (WHO) ከአንድ ዓመት በፊት ካወጣው ሪፖርት ያስታወቀ ሲሆን ፣ ድርጅቱ ብቸኝነትን በየዓመቱ ከ871ሺህ በላይ ሰዎችን ያለዕድሜ የሚቀጥፍ ዓለም አቀፍ የጤና ስጋት አድርጎ ፈርጆታል።
በተጨማሪም፤ ከልብ በሽታ፣ ስትሮክ እና ድብርት ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት ያለው ይህ አሳሳቢ ችግር በየሰዓቱ 100 ሰዎችን ለሞት እንደሚዳርግ መግለጹ አይዘነጋም።
በመሆኑም የህክምና ባለሙያዎች 'የብቸኝነት' እንደ አእምሮ ጤና ጉዳይ ብቻ ሳይሆን፤ የልብ እና የደም ስር የጤና ስጋት በመሆኑ ተገቢውን ትኩረት ሊሰጠው እንደሚገባ በጥናቱ አጽኖት ተሰጥቷል።
Seledadotio
Seledadotio
ብቸኝነት የአእምሮ ጤና ጉዳይ ብቻ ሳይሆን፤ የልብን መዋቅር በቀጥታ በመጉዳት ለከፋ የጤና ችግር የሚያጋልጥ አሳሳቢ ችግር መሆኑን በአሜሪካ የልብ ማህበር (AHA) ይፋ የተደረገ አንድ አዲስ ጥናት አመላክቷል።
ጥናቱ እንዳመለከተው፣ ብቸኝነት የሰውነትን የጭንቀት መጠንን በመጨመር የጭንቀት ሆርሞኖች (እንደ ኮርቲሶል ያሉ) በሰውነታችን ውስጥ እንዲጨምሩ ያደርጋል።
ይህ ከብቸኝነት የሚመነጭ ስነ-ልቦናዊ እና ማህበራዊ ጭንቀት ደግሞ፣ በጊዜ ሂደት የልብ ቫልቭን (Heart Valve) በመጉዳት ለከፋ የልብ ጤና መቃወስ እንደሚያጋልጥ በካሊፎርኒያ ዩኒቨርሲቲ የተመራው ይህ የጥናት ቡድንአረጋግጧል።
በካሊፎርኒያ ዩኒቨርሲቲ ሀኪም የሆኑት ዶክተር ክሪስታል ዋይሊ ሴኔ እንዳሉት፤ “የህክምና ባለሙያዎች ታካሚዎቻቸውን ስለ ማህበራዊ ግንኙነቶቻቸው ሊጠይቋቸው ይገባል፤ ይህን አለማድረግ ታካሚዎችን ለከፋ የልብ ጤና እክል አልፎ ተርፎም ለሞት ሊያጋልጣቸው ይችላል" ሲሉ አስጠንቅቀዋል።
በተጨማሪም ብቸኛ የሆኑ ሰዎች ሲጋራ ማጨስን፣ ከመጠን በላይ አልኮል መጠጣትን እና የአካል ብቃት እንቅስቃሴ አለማድረግን የመሳሰሉ ጤናማ ያልሆኑ የአኗኗር ዘይቤዎችን በብዛት ስለሚከተሉ፣ ይህ ልምምድ ለልብ እና የደም ስር ጉዳት መፋጠን ተጨማሪ ምክንያት መሆኑ ተጠቁሟል።
የአሜሪካ ዋና የቀዶ ጥገና ሀኪም በፈረጆቹ 2023 ብቸኝነትን "የህዝብ ጤና ወረርሽኝ" ሲሉ ያወጁት ሲሆን፤ ችግሩ ያለዕድሜ የመሞት አደጋን በ26 በመቶ ከፍ እንደሚያደርገውና ይህም በቀን 15 ሲጋራዎችን ከማጨስ ጋር እኩል የሚመዘን ጉዳት እንዳለው መግለጻቸው ይታወሳል።
ይህ የችግሩ አሳሳቢነት የዓለም ጤና ድርጅት (WHO) ከአንድ ዓመት በፊት ካወጣው ሪፖርት ያስታወቀ ሲሆን ፣ ድርጅቱ ብቸኝነትን በየዓመቱ ከ871ሺህ በላይ ሰዎችን ያለዕድሜ የሚቀጥፍ ዓለም አቀፍ የጤና ስጋት አድርጎ ፈርጆታል።
በተጨማሪም፤ ከልብ በሽታ፣ ስትሮክ እና ድብርት ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት ያለው ይህ አሳሳቢ ችግር በየሰዓቱ 100 ሰዎችን ለሞት እንደሚዳርግ መግለጹ አይዘነጋም።
በመሆኑም የህክምና ባለሙያዎች 'የብቸኝነት' እንደ አእምሮ ጤና ጉዳይ ብቻ ሳይሆን፤ የልብ እና የደም ስር የጤና ስጋት በመሆኑ ተገቢውን ትኩረት ሊሰጠው እንደሚገባ በጥናቱ አጽኖት ተሰጥቷል።
Seledadotio
Seledadotio
10 days ago
ባሳለፍነው የፈረንጆቹ 2025 አመት ላይ 1.3 ሚሊዮን ሰዎች የጉበት በሽታ እንዳለባቸው ሳያውቁ ህይወታቸው ማለፉ ተነገረ።
#ethiopia | በዓለም ዙሪያ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎችን ሕይወት አደጋ ላይ የጣለውና ዝምተኛ ገዳይ በመባል የሚጠራው የሄፓታይቲስ የጉበት በሽታ ስርጭት ከፍተኛ ደረጃ መድረሱ የአለም ጤና ድርጅት ተናግሯል።
የዓለም ጤና ድርጅት ይፋ ባደረገው መረጃ መሠረት 287 ሚሊዮን የሚሆን የዓለም ሕዝብ በከባድ የሄፓታይቲስ "ቢ" እና "ሲ" ቫይረሶች ተይዞ ይገኛል ብሏል።
ሆኖም ግን ከእነዚህ መካከል አብዛኞቹ በደማቸው ውስጥ ቫይረሱ መኖሩን እንኳ እንደማያውቁ ነው የገለፀው።
በሽታው አስቀድሞ መከላከልና መታከም እንዲሁም ሙሉ በሙሉ መዳን የሚችል ቢሆንም ባለፈው ዓመት ብቻ 1.3 ሚሊዮን ሰዎች በዚሁ በሽታ ምክንያት ሕይወታቸውን ማጣታቸውን ገልጿል።
በፈረንጆቹ 2024 በአለም ዙርያ ከተወለዱ ህፃናት መካከል 45 በመቶ የሚሆኑት ብቻ ናቸው በተወለዱ በ24 ሰዓታት ውስጥ የመጀመሪያ የሄፓታይቲስ "ቢ" ክትባት ያገኙት ቀሪዎቹ አላገኙም ብሏል።
የአለም ጤና ድርጅት በየአመቱ ሃምሌ 21 ቀን የሚያከብረው ዓለም አቀፍ የጉበት በሽታ ቀን በነገው እለት እንደሚከበር ገልጿል።
አዲስ የሚወለዱ ሕፃናት በተወለዱ በ24 ሰዓታት ውስጥ የመጀመርያ ደረጃ ክትባት ማግኘታቸውን ማረጋገጥ እንደሚያስፈልጋ ድርጅቱ አስታውቋል።
ማንኛውም ሰው ቀደም ብሎ በሽታው ተመርምሮ የማያውቅ ከሆነ ወይም ለአደጋው ተጋላጭ ከሆነ አሁኑኑ የሄፓታይቲስ "ቢ" እና "ሲ" ምርመራ እንዲያደርግ አሳስቧል።
ሔኖክ ወ/ገብርኤል
#ethiopia #getutemesgen #getunews #who #worldhepatitisday #vaccine
#ethiopia | በዓለም ዙሪያ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎችን ሕይወት አደጋ ላይ የጣለውና ዝምተኛ ገዳይ በመባል የሚጠራው የሄፓታይቲስ የጉበት በሽታ ስርጭት ከፍተኛ ደረጃ መድረሱ የአለም ጤና ድርጅት ተናግሯል።
የዓለም ጤና ድርጅት ይፋ ባደረገው መረጃ መሠረት 287 ሚሊዮን የሚሆን የዓለም ሕዝብ በከባድ የሄፓታይቲስ "ቢ" እና "ሲ" ቫይረሶች ተይዞ ይገኛል ብሏል።
ሆኖም ግን ከእነዚህ መካከል አብዛኞቹ በደማቸው ውስጥ ቫይረሱ መኖሩን እንኳ እንደማያውቁ ነው የገለፀው።
በሽታው አስቀድሞ መከላከልና መታከም እንዲሁም ሙሉ በሙሉ መዳን የሚችል ቢሆንም ባለፈው ዓመት ብቻ 1.3 ሚሊዮን ሰዎች በዚሁ በሽታ ምክንያት ሕይወታቸውን ማጣታቸውን ገልጿል።
በፈረንጆቹ 2024 በአለም ዙርያ ከተወለዱ ህፃናት መካከል 45 በመቶ የሚሆኑት ብቻ ናቸው በተወለዱ በ24 ሰዓታት ውስጥ የመጀመሪያ የሄፓታይቲስ "ቢ" ክትባት ያገኙት ቀሪዎቹ አላገኙም ብሏል።
የአለም ጤና ድርጅት በየአመቱ ሃምሌ 21 ቀን የሚያከብረው ዓለም አቀፍ የጉበት በሽታ ቀን በነገው እለት እንደሚከበር ገልጿል።
አዲስ የሚወለዱ ሕፃናት በተወለዱ በ24 ሰዓታት ውስጥ የመጀመርያ ደረጃ ክትባት ማግኘታቸውን ማረጋገጥ እንደሚያስፈልጋ ድርጅቱ አስታውቋል።
ማንኛውም ሰው ቀደም ብሎ በሽታው ተመርምሮ የማያውቅ ከሆነ ወይም ለአደጋው ተጋላጭ ከሆነ አሁኑኑ የሄፓታይቲስ "ቢ" እና "ሲ" ምርመራ እንዲያደርግ አሳስቧል።
ሔኖክ ወ/ገብርኤል
#ethiopia #getutemesgen #getunews #who #worldhepatitisday #vaccine
Sponsored by
Surafel
10 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) በኢትዮጵያ እያሻቀበ የመጣው የኑሮ ውድነት እና የዋጋ ግሽበት፣ 92 ሚሊዮን የሚጠጋ የሀገሪቱን ሕዝብ "ጤናማ የምግብ ሥርዓት" መከተል እንዳይችል ማድረጉን የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት (ተመድ) የቅርብ ጊዜ የምግብ ዋስትና ሪፖርት ይፋ አደረገ።
ሪፖርቱ እንዳመለከተው፣ በኢትዮጵያ ጤናማ የምግብ ሥርዓትን ለማስጠበቅ በነፍስ ወከፍ የሚወጣው ወጪ በቀጠናው (ምሥራቅ አፍሪካ) ከፍተኛው ሆኗል። ባለፈው የአውሮፓውያን ዓመት (2025) በኢትዮጵያ አንድ ሰው ጤናማ ምግብ ለማግኘት በቀን 4 ነጥብ 7 ዶላር ማውጣት የነበረበት ሲሆን፣ ይህ አኃዝ ከጎረቤት ሀገራቱ ኬንያ፣ ኡጋንዳ እና ታንዛኒያ በእጅጉ የላቀ ነው።
ከፈረንጆቹ 2023 እስከ 2025 ባለው ጊዜ ውስጥም 60 በመቶ የሚሆነው ኢትዮጵያዊ "መካከለኛ" እና "ከፍተኛ" የምግብ ዋስትና እጦት ገጥሞት እንደነበር ሪፖርቱ አብራርቷል። ይሁን እንጂ ይህ የተመድ ሪፖርት ባለፉት ዓመታት በጦርነት ክፉኛ የተጎዳውን የትግራይ ክልል መረጃ ያላካተተ በመሆኑ፣ ሀገራዊ የምግብ ቀውሱ አኃዝ ሪፖርቱ ካቀረበው እጅግ የከፋ ሊሆን እንደሚችል የኢኮኖሚ ባለሙያዎች ይገምታሉ።
ይህ የተመድ ሪፖርት የሚያሳየው የኢትዮጵያ ማክሮ ኢኮኖሚ ቀውስ በዜጎች የእለት ተእለት ህይወት እና ጤና ላይ እያደረሰ ያለውን አውዳሚ ተጽእኖ ነው። አንድ ኢትዮጵያዊ ጤናማ ምግብ ለመመገብ በቀን 4.7 ዶላር (በወቅቱ የባንክ ምንዛሪ ወደ 500 ብር ገደማ) ማውጣት አለበት ማለት፣ አብዛኛው የሀገሪቱ ህዝብ በቀን ከሚያገኘው አጠቃላይ ገቢ በእጅጉ የላቀ ነው።
ይህ የዋጋ ንረት ሀገሪቱ በግብርናው ዘርፍ እያመጣች ነው ከምትለው የምርት እድገት ትርክት ጋር በእጅጉ ይቃረናል። በተጨማሪም 92 ሚሊዮን ህዝብ (ከ80 በመቶ በላይ የሚሆነው ዜጋ) ጤናማ ምግብ የማግኘት አቅም የለውም ማለት፤ ሀገሪቱ ወደፊት ለከፍተኛ የተመጣጠነ ምግብ እጥረት፣ በሽታ እና ተያያዥ ማህበራዊ ቀውሶች እየተጋለጠች መሆኑን ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ አደገኛ አመልካች ነው። መንግስት የፖለቲካ እና የጸጥታ ቀውሶችን ፈትቶ ምርታማነትን ካላሳደገ እና የዋጋ ግሽበቱን መቆጣጠር ካልቻለ፣ ይህ የምግብ ዋስትና እጦት ወደ ሀገራዊ የህልውና አደጋ ማምራቱ የማይቀር መሆኑን ይህ ክስተት በግልጽ ያሳስባል።
ሪፖርቱ እንዳመለከተው፣ በኢትዮጵያ ጤናማ የምግብ ሥርዓትን ለማስጠበቅ በነፍስ ወከፍ የሚወጣው ወጪ በቀጠናው (ምሥራቅ አፍሪካ) ከፍተኛው ሆኗል። ባለፈው የአውሮፓውያን ዓመት (2025) በኢትዮጵያ አንድ ሰው ጤናማ ምግብ ለማግኘት በቀን 4 ነጥብ 7 ዶላር ማውጣት የነበረበት ሲሆን፣ ይህ አኃዝ ከጎረቤት ሀገራቱ ኬንያ፣ ኡጋንዳ እና ታንዛኒያ በእጅጉ የላቀ ነው።
ከፈረንጆቹ 2023 እስከ 2025 ባለው ጊዜ ውስጥም 60 በመቶ የሚሆነው ኢትዮጵያዊ "መካከለኛ" እና "ከፍተኛ" የምግብ ዋስትና እጦት ገጥሞት እንደነበር ሪፖርቱ አብራርቷል። ይሁን እንጂ ይህ የተመድ ሪፖርት ባለፉት ዓመታት በጦርነት ክፉኛ የተጎዳውን የትግራይ ክልል መረጃ ያላካተተ በመሆኑ፣ ሀገራዊ የምግብ ቀውሱ አኃዝ ሪፖርቱ ካቀረበው እጅግ የከፋ ሊሆን እንደሚችል የኢኮኖሚ ባለሙያዎች ይገምታሉ።
ይህ የተመድ ሪፖርት የሚያሳየው የኢትዮጵያ ማክሮ ኢኮኖሚ ቀውስ በዜጎች የእለት ተእለት ህይወት እና ጤና ላይ እያደረሰ ያለውን አውዳሚ ተጽእኖ ነው። አንድ ኢትዮጵያዊ ጤናማ ምግብ ለመመገብ በቀን 4.7 ዶላር (በወቅቱ የባንክ ምንዛሪ ወደ 500 ብር ገደማ) ማውጣት አለበት ማለት፣ አብዛኛው የሀገሪቱ ህዝብ በቀን ከሚያገኘው አጠቃላይ ገቢ በእጅጉ የላቀ ነው።
ይህ የዋጋ ንረት ሀገሪቱ በግብርናው ዘርፍ እያመጣች ነው ከምትለው የምርት እድገት ትርክት ጋር በእጅጉ ይቃረናል። በተጨማሪም 92 ሚሊዮን ህዝብ (ከ80 በመቶ በላይ የሚሆነው ዜጋ) ጤናማ ምግብ የማግኘት አቅም የለውም ማለት፤ ሀገሪቱ ወደፊት ለከፍተኛ የተመጣጠነ ምግብ እጥረት፣ በሽታ እና ተያያዥ ማህበራዊ ቀውሶች እየተጋለጠች መሆኑን ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ አደገኛ አመልካች ነው። መንግስት የፖለቲካ እና የጸጥታ ቀውሶችን ፈትቶ ምርታማነትን ካላሳደገ እና የዋጋ ግሽበቱን መቆጣጠር ካልቻለ፣ ይህ የምግብ ዋስትና እጦት ወደ ሀገራዊ የህልውና አደጋ ማምራቱ የማይቀር መሆኑን ይህ ክስተት በግልጽ ያሳስባል።
10 days ago
በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ከ23 ነጥብ 2 ሚሊየን ኩንታል በላይ ምርት ተሰበሰበ
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 20፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል በ2018 በጀት ዓመት ከ23 ነጥብ 2 ሚሊየን ኩንታል በላይ ምርት ተሰብስቧል አሉ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)።
ርዕሰ መስተዳድር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) በክልሉ በ2018 በጀት ዓመት በግብርና ዘርፍ የላቀ አፈጻጸም መመዝገቡን ገልጸዋል፡፡
በዚህም በእርሻ ዘርፍ በሁሉም የምርት ወቅቶች ከ801 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑንና የምርት ዕድገቱም ከ2014 መነሻ ዓመት ጋር ሲነጻጸር በ60 ነጥብ 3 በመቶ ማደጉን አስረድተዋል።
በተጨማሪም በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት ከ5 ሺህ 700 ሄክታር በላይ ማሳ በማልማት ከ192 ሺህ ኩንታል በላይ ምርት መሰብሰብ መቻሉን አመልክተዋል።
ርዕሰ መስተዳድሩ በእንስሳትና ዓሳ ሀብት ልማት ዘርፍ በሌማት ትሩፋት መርሐ ግብር 390 ሚሊየን ሊትር የወተት፣ 362 ሚሊየን እንቁላል፣ 79 ሺህ ቶን በላይ የማርና 81 ሺህ ቶን በላይ የስጋ ምርት ለገበያ ማቅረብ መቻሉንም አመልክተዋል።
ከ61 ሺህ ቶን በላይ ቡና ወደ ማዕከላዊ ገበያ በመላክ ከመነሻ ዓመቱ የ74 በመቶ እድገት መመዝገቡንና በሕገ ወጥ ቡና ዝውውር ቁጥጥርም 33 ሚሊየን ብር ወደ መንግሥት ካዝና ገቢ ማድረግ መቻሉን አብራርተዋል።
የኅብረት ሥራ ማህበራት ከወጪ ንግድ 2 ነጥብ 89 ሚሊየን ዶላር ያስገኙ ሲሆን፤ በአደጋ ስጋት ሥራ አመራርም 86 በመቶ የሴፍቲኔት ተጠቃሚዎችን ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ማሸጋገር ተችሏል ነው ያሉት።
በሰብል ምርምር 19 የገብስ ዘረ መሎች የተሰበሰቡ ሲሆን በአጃ፣ ሩዝ እና በተሻሻሉ የጤፍ ዝርያዎች ምርታማነት ላይ የሙከራ ጥናቶች መካሄዱን ገልጸዋል፡፡
በሌላ በኩል የገንዲ በሽታ ስጋት ጠቋሚ ካርታ የተዘጋጀ ሲሆን፤ በማህበረሰብ አቀፍ የእንስሳት ዝርያ ማሻሻያ ፕሮጀክት 1 ሺህ 22 የዘር በጎች ተመርጠው 831 የተሻሻሉ በጎች ለአርሶ አደሩ መሰራጨታቸውን አንስተዋል።
በመጥፋት ላይ ያሉ ሀገር በቀል ዛፎችንና የሸኮ ዳልጋ ከብት ዝርያን የመጠበቅ ሥራ ተከናውኗል ነው ያሉት።
ከ88 ነጥብ 5 ሚሊየን በላይ ችግኞችን በመትከል ከ20 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በማልማት የደን ሽፋኑን ከ43 ነጥብ 85 በመቶ ወደ 44 ነጥብ 65 በመቶ ማሳደግ የተቻለ ሲሆን፤ ከደን ውጤቶችም ከ11 ነጥብ 8 ሚሊየን ብር በላይ የሮያሊቲ ክፍያ መሰብሰቡን አመልክተዋል።
የከተሞችን የቆሻሻ ችግር ለመቅረፍ በርካታ ስራ መሰራቱን ጠቅሰው ለ509 አዳዲስ የልማት ፕሮጀክቶች የአካባቢና ማህበራዊ ተፅዕኖ ግምገማ ይሁንታ ፈቃድ መሰጠቱን የክልሉ ኮሙኒኬሽን ለፋና ዲጂታል የላከው መረጃ ያመላክታል።
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 20፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል በ2018 በጀት ዓመት ከ23 ነጥብ 2 ሚሊየን ኩንታል በላይ ምርት ተሰብስቧል አሉ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)።
ርዕሰ መስተዳድር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) በክልሉ በ2018 በጀት ዓመት በግብርና ዘርፍ የላቀ አፈጻጸም መመዝገቡን ገልጸዋል፡፡
በዚህም በእርሻ ዘርፍ በሁሉም የምርት ወቅቶች ከ801 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑንና የምርት ዕድገቱም ከ2014 መነሻ ዓመት ጋር ሲነጻጸር በ60 ነጥብ 3 በመቶ ማደጉን አስረድተዋል።
በተጨማሪም በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት ከ5 ሺህ 700 ሄክታር በላይ ማሳ በማልማት ከ192 ሺህ ኩንታል በላይ ምርት መሰብሰብ መቻሉን አመልክተዋል።
ርዕሰ መስተዳድሩ በእንስሳትና ዓሳ ሀብት ልማት ዘርፍ በሌማት ትሩፋት መርሐ ግብር 390 ሚሊየን ሊትር የወተት፣ 362 ሚሊየን እንቁላል፣ 79 ሺህ ቶን በላይ የማርና 81 ሺህ ቶን በላይ የስጋ ምርት ለገበያ ማቅረብ መቻሉንም አመልክተዋል።
ከ61 ሺህ ቶን በላይ ቡና ወደ ማዕከላዊ ገበያ በመላክ ከመነሻ ዓመቱ የ74 በመቶ እድገት መመዝገቡንና በሕገ ወጥ ቡና ዝውውር ቁጥጥርም 33 ሚሊየን ብር ወደ መንግሥት ካዝና ገቢ ማድረግ መቻሉን አብራርተዋል።
የኅብረት ሥራ ማህበራት ከወጪ ንግድ 2 ነጥብ 89 ሚሊየን ዶላር ያስገኙ ሲሆን፤ በአደጋ ስጋት ሥራ አመራርም 86 በመቶ የሴፍቲኔት ተጠቃሚዎችን ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ማሸጋገር ተችሏል ነው ያሉት።
በሰብል ምርምር 19 የገብስ ዘረ መሎች የተሰበሰቡ ሲሆን በአጃ፣ ሩዝ እና በተሻሻሉ የጤፍ ዝርያዎች ምርታማነት ላይ የሙከራ ጥናቶች መካሄዱን ገልጸዋል፡፡
በሌላ በኩል የገንዲ በሽታ ስጋት ጠቋሚ ካርታ የተዘጋጀ ሲሆን፤ በማህበረሰብ አቀፍ የእንስሳት ዝርያ ማሻሻያ ፕሮጀክት 1 ሺህ 22 የዘር በጎች ተመርጠው 831 የተሻሻሉ በጎች ለአርሶ አደሩ መሰራጨታቸውን አንስተዋል።
በመጥፋት ላይ ያሉ ሀገር በቀል ዛፎችንና የሸኮ ዳልጋ ከብት ዝርያን የመጠበቅ ሥራ ተከናውኗል ነው ያሉት።
ከ88 ነጥብ 5 ሚሊየን በላይ ችግኞችን በመትከል ከ20 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በማልማት የደን ሽፋኑን ከ43 ነጥብ 85 በመቶ ወደ 44 ነጥብ 65 በመቶ ማሳደግ የተቻለ ሲሆን፤ ከደን ውጤቶችም ከ11 ነጥብ 8 ሚሊየን ብር በላይ የሮያሊቲ ክፍያ መሰብሰቡን አመልክተዋል።
የከተሞችን የቆሻሻ ችግር ለመቅረፍ በርካታ ስራ መሰራቱን ጠቅሰው ለ509 አዳዲስ የልማት ፕሮጀክቶች የአካባቢና ማህበራዊ ተፅዕኖ ግምገማ ይሁንታ ፈቃድ መሰጠቱን የክልሉ ኮሙኒኬሽን ለፋና ዲጂታል የላከው መረጃ ያመላክታል።
14 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) በኬንያ ማርሳቢት ካውንቲ ሞያሌ ከተማ ውስጥ ለአንድ መኖሪያ ቤት መሠረት ሲቆፈር፣ ከጣሊያን የኢትዮጵያ ወረራ (ከ1935–1936 እ.ኤ.አ) ዘመን ጀምሮ መሬት ውስጥ ተቀብረው የቆዩ ከ4,000 በላይ ጥይቶች መገኘታቸውን የኬንያ ፖሊስ አስታወቀ።
እንደ ፖሊስ መረጃ ጥይቶቹ የተገኙት በሞያሌ ከተማ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ፊት ለፊት በሚገኝ ቦታ ላይ ለአንድ ቤት መሠረት የማውጣት ሥራ ሲካሄድ ነው። መሬት ውስጥ የተቀበሩ በርካታ የብረት ቁሳቁሶችን የተመለከተው የአካባቢው ነዋሪ ጥይት መሆናቸውን በመጠራጠር ለደኅንነት አካላት ጥቆማ ሰጥቷል። የደኅንነት አባላት በቦታው ተገኝተው ባደረጉት ቁፋሮ 4,060 የሚያክሉ 8×50 ሚሊሜትር መጠን ያላቸው ጥይቶችን ማውጣት ተችሏል። ጥይቶቹ የቀደመው የጣሊያን ጦር በወቅቱ በነበረው የጦርነት ዘመቻ ወቅት ጥሏቸው የሄዳቸው እንደሆኑ የተገመተ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት ወደ ሞያሌ ፖሊስ ጣቢያ የጦር መሣሪያ ግምጃ ቤት ተዘዋውረው በጥንቃቄ እንዲወገዱ መደረጉ ተገልጿል።
በሌላ በኩል በዚሁ ማርሳቢት ካውንቲ ቻልቢ በረሃ አቅራቢያ በሚገኘው ኮሮሌ በተባለ ቦታ አቅራቢያ የሚገኙ ጥንታዊ መቃብሮች መገኘታቸውን ተከትሎ ፖሊስ ምርመራ መጀመሩን አስታውቋል። በቁጥር 50 የሚሆኑት እነዚህ መቃብሮች የተገኙት በአንድ እረኛ አማካኝነት ሲሆን፣ የአካባቢው ነዋሪዎች እና የ75 ዓመቱ አረጋዊ ኤድዋርድ እንደተናገሩት፣ ቦታው በ1935 እ.ኤ.አ ጣሊያን ኢትዮጵያን በወረረችበት ወቅት ተይዘው በብሪታንያ ቅኝ ግዛት ስር የነበሩ የኢትዮጵያውያን ተፈናቃዮች እና ስደተኞች መጠለያ የነበረ ነው።
በወቅቱ በርካታ ኢትዮጵያውያን በበሽታ እና በውኃ እጥረት ምክንያት ሕይወታቸው አልፎ እዚያው ቦታ መቃበራቸውን አረጋዊው ገልጸዋል። የኬንያ ፖሊስ እና የአካባቢው አስተዳደር አካላት ቦታውን በመጠበቅ የታሪካዊነቱን መጠን እና የመቃብሮቹን ዝርዝር ሁኔታ የሚያጣራ ተጨማሪ ጥናት እያካሄዱ ይገኛሉ።
የጸጥታ አካላት በሕዝብ ደኅንነት ላይ ምንም ዓይነት አደጋ አለመኖሩን ያረጋገጡ ሲሆን፣ ነዋሪዎች መሰል የቆዩ የጦር መሣሪያዎች ወይም ጥይቶች ሲያገኙ በራሳቸው ከመንካት ይልቅ በአስቸኳይ ለፖሊስ ጥቆማ እንዲሰጡ አሳስበዋል።
እንደ ፖሊስ መረጃ ጥይቶቹ የተገኙት በሞያሌ ከተማ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ፊት ለፊት በሚገኝ ቦታ ላይ ለአንድ ቤት መሠረት የማውጣት ሥራ ሲካሄድ ነው። መሬት ውስጥ የተቀበሩ በርካታ የብረት ቁሳቁሶችን የተመለከተው የአካባቢው ነዋሪ ጥይት መሆናቸውን በመጠራጠር ለደኅንነት አካላት ጥቆማ ሰጥቷል። የደኅንነት አባላት በቦታው ተገኝተው ባደረጉት ቁፋሮ 4,060 የሚያክሉ 8×50 ሚሊሜትር መጠን ያላቸው ጥይቶችን ማውጣት ተችሏል። ጥይቶቹ የቀደመው የጣሊያን ጦር በወቅቱ በነበረው የጦርነት ዘመቻ ወቅት ጥሏቸው የሄዳቸው እንደሆኑ የተገመተ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት ወደ ሞያሌ ፖሊስ ጣቢያ የጦር መሣሪያ ግምጃ ቤት ተዘዋውረው በጥንቃቄ እንዲወገዱ መደረጉ ተገልጿል።
በሌላ በኩል በዚሁ ማርሳቢት ካውንቲ ቻልቢ በረሃ አቅራቢያ በሚገኘው ኮሮሌ በተባለ ቦታ አቅራቢያ የሚገኙ ጥንታዊ መቃብሮች መገኘታቸውን ተከትሎ ፖሊስ ምርመራ መጀመሩን አስታውቋል። በቁጥር 50 የሚሆኑት እነዚህ መቃብሮች የተገኙት በአንድ እረኛ አማካኝነት ሲሆን፣ የአካባቢው ነዋሪዎች እና የ75 ዓመቱ አረጋዊ ኤድዋርድ እንደተናገሩት፣ ቦታው በ1935 እ.ኤ.አ ጣሊያን ኢትዮጵያን በወረረችበት ወቅት ተይዘው በብሪታንያ ቅኝ ግዛት ስር የነበሩ የኢትዮጵያውያን ተፈናቃዮች እና ስደተኞች መጠለያ የነበረ ነው።
በወቅቱ በርካታ ኢትዮጵያውያን በበሽታ እና በውኃ እጥረት ምክንያት ሕይወታቸው አልፎ እዚያው ቦታ መቃበራቸውን አረጋዊው ገልጸዋል። የኬንያ ፖሊስ እና የአካባቢው አስተዳደር አካላት ቦታውን በመጠበቅ የታሪካዊነቱን መጠን እና የመቃብሮቹን ዝርዝር ሁኔታ የሚያጣራ ተጨማሪ ጥናት እያካሄዱ ይገኛሉ።
የጸጥታ አካላት በሕዝብ ደኅንነት ላይ ምንም ዓይነት አደጋ አለመኖሩን ያረጋገጡ ሲሆን፣ ነዋሪዎች መሰል የቆዩ የጦር መሣሪያዎች ወይም ጥይቶች ሲያገኙ በራሳቸው ከመንካት ይልቅ በአስቸኳይ ለፖሊስ ጥቆማ እንዲሰጡ አሳስበዋል።
15 days ago
የወረቀት ሳሙናን ለገበያ ያቀረበችው የባቲ ከተማዋ ወጣት
ባቲ፣ ኢትዮጵያ — አብዛኞቻችን ሳሙናን በደረቅ (በቁራጭ)፣ በዱቄት ወይም በፈሳሽ መልክ ብቻ አውቀን ለለመድነው አጠቃቀም፣ የባቲ ከተማ ነዋሪዋ ወጣት ኢክራም ሙሐመድ አዲስና ምቹ አማራጭ ይዛ ብቅ ብላለች።
ወጣቷ ከአካባቢዋ ችግሮች በመነሳት ለእጅ መታጠቢያ የሚሆን «የወረቀት ሳሙና» በመፍጠር የብዙዎችን ትኩረት ስባለች።
ኢክራም ለዚህ የፈጠራ ሥራዋ መነሻ የሆነውን አጋጣሚ ስታብራራ፤ በተለያዩ ቦታዎች ለስራና ለጉዞ በሚንቀሳቀሱበት ወቅት እጅ ለመታጠብ የሚሆን ሳሙና ማጣት የተለመደ ፈተና በመሆኑ፣ ይህንን ክፍተት የሚሞላ መፍትሔ ለመፈለግ መነሳቷን ትናገራለች።
ይህ የወረቀት ሳሙና ከባህላዊ የሳሙና አይነቶች የሚለዩት በርካታ አዎንታዊ ጎኖች አሉት፦
* ቀደም ሲል ከምናውቃቸውና ለተላላፊ በሽታዎች ሊያጋልጡ ከሚችሉ የጋራ መጠቀሚያ ሳሙናዎች በተለየ፣ እያንዳንዱ ሰው ለብቻው በግል ለመጠቀም በሚመች መልኩ የተዘጋጀ ነው።
* በቦታ፣ በሁኔታዎችና በቦርሳ ጥበት ሳይገደቡ በየትኛውም ስፍራ ይዞ ለመንቀሳቀስ እና ለመጠቀም አጅግ ምቹ ነው።
* ከአንዱ ጥቅል ላይ አንድ ቀጭን ወረቀት በመለየት በእጅ ላይ አድርጎ በጥቂት ውሃ በማሸት ብቻ በቀላሉ መጠቀም ይቻላል።
ምርቱን ለማዘጋጀት በአካባቢዋ በቀላሉ የሚገኙ ጥሬ እቃዎችን የተጠቀመች ሲሆን፣ የእጅ ቆዳን በማይጎዳ መልኩ የኬሚካል ውህዶችን በራሷ በማቀናጀት ለወረቀት ሳሙናው የሚፈለገውን ቅርጽ አስይዛዋለች። ለዚህ ስኬቷም የአባቷ እገዛና ድጋፍ ከፍተኛ እንደነበረ ትገልጻለች።
ምርቷን በአካባቢዋ መጠሪያ «ገንደዳዩ» በሚል ስያሜ ሰይማ ወደ ገበያ ያቀረበችው ወጣት ኢክራም፤ በተለያዩ ባዛሮች ላይ በማሳተፍ ከተጠቃሚዎች እጅግ አዎንታዊ እና አበረታች ግብረ-መልስ ማግኘቷን ተናግራለች።
በቀጣይም የዚሁን የወረቀት ሳሙና ጥራትና መጠን በከፍተኛ ደረጃ በመጨመር በስፋት ለሀገር ውስጥ ገበያ ለማቅረብ ጠንክራ እየሰራች እንደሆነና የወደፊት አላማዋም ምርቱን ማስፋፋት እንደሆነ ገልጻለች።
Via አሚኮ
Seledadotio
Seledadotio
ባቲ፣ ኢትዮጵያ — አብዛኞቻችን ሳሙናን በደረቅ (በቁራጭ)፣ በዱቄት ወይም በፈሳሽ መልክ ብቻ አውቀን ለለመድነው አጠቃቀም፣ የባቲ ከተማ ነዋሪዋ ወጣት ኢክራም ሙሐመድ አዲስና ምቹ አማራጭ ይዛ ብቅ ብላለች።
ወጣቷ ከአካባቢዋ ችግሮች በመነሳት ለእጅ መታጠቢያ የሚሆን «የወረቀት ሳሙና» በመፍጠር የብዙዎችን ትኩረት ስባለች።
ኢክራም ለዚህ የፈጠራ ሥራዋ መነሻ የሆነውን አጋጣሚ ስታብራራ፤ በተለያዩ ቦታዎች ለስራና ለጉዞ በሚንቀሳቀሱበት ወቅት እጅ ለመታጠብ የሚሆን ሳሙና ማጣት የተለመደ ፈተና በመሆኑ፣ ይህንን ክፍተት የሚሞላ መፍትሔ ለመፈለግ መነሳቷን ትናገራለች።
ይህ የወረቀት ሳሙና ከባህላዊ የሳሙና አይነቶች የሚለዩት በርካታ አዎንታዊ ጎኖች አሉት፦
* ቀደም ሲል ከምናውቃቸውና ለተላላፊ በሽታዎች ሊያጋልጡ ከሚችሉ የጋራ መጠቀሚያ ሳሙናዎች በተለየ፣ እያንዳንዱ ሰው ለብቻው በግል ለመጠቀም በሚመች መልኩ የተዘጋጀ ነው።
* በቦታ፣ በሁኔታዎችና በቦርሳ ጥበት ሳይገደቡ በየትኛውም ስፍራ ይዞ ለመንቀሳቀስ እና ለመጠቀም አጅግ ምቹ ነው።
* ከአንዱ ጥቅል ላይ አንድ ቀጭን ወረቀት በመለየት በእጅ ላይ አድርጎ በጥቂት ውሃ በማሸት ብቻ በቀላሉ መጠቀም ይቻላል።
ምርቱን ለማዘጋጀት በአካባቢዋ በቀላሉ የሚገኙ ጥሬ እቃዎችን የተጠቀመች ሲሆን፣ የእጅ ቆዳን በማይጎዳ መልኩ የኬሚካል ውህዶችን በራሷ በማቀናጀት ለወረቀት ሳሙናው የሚፈለገውን ቅርጽ አስይዛዋለች። ለዚህ ስኬቷም የአባቷ እገዛና ድጋፍ ከፍተኛ እንደነበረ ትገልጻለች።
ምርቷን በአካባቢዋ መጠሪያ «ገንደዳዩ» በሚል ስያሜ ሰይማ ወደ ገበያ ያቀረበችው ወጣት ኢክራም፤ በተለያዩ ባዛሮች ላይ በማሳተፍ ከተጠቃሚዎች እጅግ አዎንታዊ እና አበረታች ግብረ-መልስ ማግኘቷን ተናግራለች።
በቀጣይም የዚሁን የወረቀት ሳሙና ጥራትና መጠን በከፍተኛ ደረጃ በመጨመር በስፋት ለሀገር ውስጥ ገበያ ለማቅረብ ጠንክራ እየሰራች እንደሆነና የወደፊት አላማዋም ምርቱን ማስፋፋት እንደሆነ ገልጻለች።
Via አሚኮ
Seledadotio
Seledadotio
16 days ago
እየተባባሰ የመጣው የኦንላይን ማጭበርበር
በማኅበራዊ ሚዲያዎች " ውጭ ሀገር እኖራለሁ " ፣ " የፍቅር ጓደኛ እፈልጋለሁ " ወይም " ለሞት የሚዳርግ በሽታ ይዞኛል፤ ሀብቴን የሚያስተዳድርልኝ ታማኝ ሰው እፈልጋለሁ " በሚሉ መልዕክቶች ተጠቃሚዎችን በማታለል እስከ 500 ሺህ ብር የሚደርስ ገንዘብ እያሳጡ መሆናቸውን የፌዴራል ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ አስታውቋል።
በጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ የተደራጁና ድንበር ተሻጋሪ ወንጀሎች ምክትል ዳይሬክተር ወ/ሮ እጣወርቅ ተስፋዬ ለሸገር ኤፍ ኤም ሬድዮ እንዳሉት፣ አጭበርባሪዎቹ ፌስቡክ፣ ዋትስአፕ እና ቴሌግራምን በመጠቀም የውሸት ማንነት በመፍጠር ተጎጂዎችን ያጠምዳሉ።
" ሀብታም ነኝ "፣ " ከሁሉም አንተን/አንቺን መርጫለሁ " የሚሉ መልዕክቶችም ከሚጠቀሙባቸው የማጭበርበሪያ ስልቶች መካከል ናቸው።
ከተጎጂዎች ጋር ግንኙነታቸውን ካጠናከሩ በኋላ፣ ሌላ ሰው በተለየ ስልክ ቁጥር በመደወል " የላክነው ዕቃ ጉምሩክ ደርሷል፤ ነገር ግን ዶላር ወይም ወርቅ ስላለበት ክፍያ ያስፈልጋል " በማለት የታሸገ ዕቃ ፎቶ በመላክ ገንዘብ እንዲልኩ እንደሚያደርጉ ተገልጿል።
በዚህ ሂደት ከ500 ሺህ እና ከዛ በላይ ገንዘብ ሰዎች እንደሚጭበረበሩ አመልክተዋል።
ወ/ሮ እጣወርቅ የማህበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች " ከሁሉም ሰው እኔ ለምን ተመረጥኩ ? " እና " ለስጦታ እንዴት ክፍያ ይጠየቃል ? " የሚሉ ጥያቄዎችን ራሳቸውን በመጠየቅ ከመሰል ማጭበርበሮች እንዲጠነቀቁ አሳስበዋል።
የኦንላይን ማጭበርበር ወንጀል እየተስፋፋ ሲሆን፣ ባለፈው የበጀት ዓመት ብቻ ከ100 ሺህ ብር በላይ ጉዳት ያስከተሉ ከ80 በላይ ዋና ዋና የክስ መዝገቦች በፌዴራል ዐቃቤ ሕግ መመስረታቸው ተገልጿል።
Seledadotio
Seledadotio
በማኅበራዊ ሚዲያዎች " ውጭ ሀገር እኖራለሁ " ፣ " የፍቅር ጓደኛ እፈልጋለሁ " ወይም " ለሞት የሚዳርግ በሽታ ይዞኛል፤ ሀብቴን የሚያስተዳድርልኝ ታማኝ ሰው እፈልጋለሁ " በሚሉ መልዕክቶች ተጠቃሚዎችን በማታለል እስከ 500 ሺህ ብር የሚደርስ ገንዘብ እያሳጡ መሆናቸውን የፌዴራል ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ አስታውቋል።
በጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ የተደራጁና ድንበር ተሻጋሪ ወንጀሎች ምክትል ዳይሬክተር ወ/ሮ እጣወርቅ ተስፋዬ ለሸገር ኤፍ ኤም ሬድዮ እንዳሉት፣ አጭበርባሪዎቹ ፌስቡክ፣ ዋትስአፕ እና ቴሌግራምን በመጠቀም የውሸት ማንነት በመፍጠር ተጎጂዎችን ያጠምዳሉ።
" ሀብታም ነኝ "፣ " ከሁሉም አንተን/አንቺን መርጫለሁ " የሚሉ መልዕክቶችም ከሚጠቀሙባቸው የማጭበርበሪያ ስልቶች መካከል ናቸው።
ከተጎጂዎች ጋር ግንኙነታቸውን ካጠናከሩ በኋላ፣ ሌላ ሰው በተለየ ስልክ ቁጥር በመደወል " የላክነው ዕቃ ጉምሩክ ደርሷል፤ ነገር ግን ዶላር ወይም ወርቅ ስላለበት ክፍያ ያስፈልጋል " በማለት የታሸገ ዕቃ ፎቶ በመላክ ገንዘብ እንዲልኩ እንደሚያደርጉ ተገልጿል።
በዚህ ሂደት ከ500 ሺህ እና ከዛ በላይ ገንዘብ ሰዎች እንደሚጭበረበሩ አመልክተዋል።
ወ/ሮ እጣወርቅ የማህበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች " ከሁሉም ሰው እኔ ለምን ተመረጥኩ ? " እና " ለስጦታ እንዴት ክፍያ ይጠየቃል ? " የሚሉ ጥያቄዎችን ራሳቸውን በመጠየቅ ከመሰል ማጭበርበሮች እንዲጠነቀቁ አሳስበዋል።
የኦንላይን ማጭበርበር ወንጀል እየተስፋፋ ሲሆን፣ ባለፈው የበጀት ዓመት ብቻ ከ100 ሺህ ብር በላይ ጉዳት ያስከተሉ ከ80 በላይ ዋና ዋና የክስ መዝገቦች በፌዴራል ዐቃቤ ሕግ መመስረታቸው ተገልጿል።
Seledadotio
Seledadotio
19 days ago
#ጤናመረጃ
የሀበሻ ጎመን ዋና ዋና የጤና ጥቅሞች!
የሀበሻ ጎመን በቪታሚኖች (C, A, K) በማዕድናት (ካልሲየም፣ ብረት) እና በፀረ-ኦክሲዳንት ንጥረ ነገሮች እጅግ የበለፀገ ነው።
1. ለአጥንት ጥንካሬና ጤንነት፦ የሀበሻ ጎመን እጅግ ከፍተኛ የካልሲየም (Calcium) እና የቪታሚን ኬ (Vitamin K) ይዘት ስላለው፣ ለአጥንት መገንባት፣ ለጥንካሬ እና የአጥንት መሳሳትን ለመከላከል አስተዋጽኦ አለው።
2. በሽታ የመከላከል አቅምን ለማጠናከር፦ በውስጡ ባለው ከፍተኛ የቪታሚን ሲ መጠን ምክንያት፣ የሰውነትን በሽታ የመከላከል ሥርዓት በማገዝ ከኢንፌክሽኖች እና ከተለያዩ በሽታዎች ይጠብቃል።
3. የደም ማነስን ለመከላከል፦ ጎመን በውስጡ ከፍተኛ የiron ማዕድን ይዟል። ይህም የሰውነታችንን ቀይ የደም ሴል ምርት በማገዝ የደም ማነስ ችግር እንዳይከሰት ትልቅ እገዛ ያደርጋል።
4. ለምግብ መፈጨት ሥርዓት፦ ልክ እንደ ጥቅል ጎመን ሁሉ፣ የሀበሻ ጎመንም ከፍተኛ የፋይበር (የቃጫ) ይዘት ስላለው የሆድ ድርቀትን ለመከላከል እና የአንጀትን ጤንነት ለመጠበቅ ይረዳል።
5. ለአይን ጤንነትና እይታ፦ በአይን ላይ የሚመጡ የዕድሜ መግፋት ጉዳቶችን እና ሌሎች የዓይን በሽታዎችን የመከላከል አቅም ያላቸውን ሉቲን እና ቪታሚን ኤ በበቂ መጠን ይዟል።
6.ለቆዳና ለፀጉር ውበት፦ በውስጡ የሚገኙት ቪታሚኖች (A,C,E) እና ፀረ-ኦክሲዳንቶች ለቆዳ ጤንነት፣ ለወጣትነት ገጽታ እና ለፀጉር ጥንካሬ አስተዋጽኦ ያደርጋሉ።
ጠቃሚ ምክር :- የሀበሻ ጎመንን ከመጠን በላይ ሳያበስሉ (ሳይሞት) በመጠኑ አብስሎ መመገብ በውስጡ ያሉትን ጠቃሚ ንጥረ ነገሮች ሙሉ በሙሉ ለማግኘት ይረዳል።(ኢትዮ-መረጃ)
ጠቃሚ ነውና ለወዳጆ ያካፍሉ! ሼር!
Seledadotio
Seledadotio
የሀበሻ ጎመን ዋና ዋና የጤና ጥቅሞች!
የሀበሻ ጎመን በቪታሚኖች (C, A, K) በማዕድናት (ካልሲየም፣ ብረት) እና በፀረ-ኦክሲዳንት ንጥረ ነገሮች እጅግ የበለፀገ ነው።
1. ለአጥንት ጥንካሬና ጤንነት፦ የሀበሻ ጎመን እጅግ ከፍተኛ የካልሲየም (Calcium) እና የቪታሚን ኬ (Vitamin K) ይዘት ስላለው፣ ለአጥንት መገንባት፣ ለጥንካሬ እና የአጥንት መሳሳትን ለመከላከል አስተዋጽኦ አለው።
2. በሽታ የመከላከል አቅምን ለማጠናከር፦ በውስጡ ባለው ከፍተኛ የቪታሚን ሲ መጠን ምክንያት፣ የሰውነትን በሽታ የመከላከል ሥርዓት በማገዝ ከኢንፌክሽኖች እና ከተለያዩ በሽታዎች ይጠብቃል።
3. የደም ማነስን ለመከላከል፦ ጎመን በውስጡ ከፍተኛ የiron ማዕድን ይዟል። ይህም የሰውነታችንን ቀይ የደም ሴል ምርት በማገዝ የደም ማነስ ችግር እንዳይከሰት ትልቅ እገዛ ያደርጋል።
4. ለምግብ መፈጨት ሥርዓት፦ ልክ እንደ ጥቅል ጎመን ሁሉ፣ የሀበሻ ጎመንም ከፍተኛ የፋይበር (የቃጫ) ይዘት ስላለው የሆድ ድርቀትን ለመከላከል እና የአንጀትን ጤንነት ለመጠበቅ ይረዳል።
5. ለአይን ጤንነትና እይታ፦ በአይን ላይ የሚመጡ የዕድሜ መግፋት ጉዳቶችን እና ሌሎች የዓይን በሽታዎችን የመከላከል አቅም ያላቸውን ሉቲን እና ቪታሚን ኤ በበቂ መጠን ይዟል።
6.ለቆዳና ለፀጉር ውበት፦ በውስጡ የሚገኙት ቪታሚኖች (A,C,E) እና ፀረ-ኦክሲዳንቶች ለቆዳ ጤንነት፣ ለወጣትነት ገጽታ እና ለፀጉር ጥንካሬ አስተዋጽኦ ያደርጋሉ።
ጠቃሚ ምክር :- የሀበሻ ጎመንን ከመጠን በላይ ሳያበስሉ (ሳይሞት) በመጠኑ አብስሎ መመገብ በውስጡ ያሉትን ጠቃሚ ንጥረ ነገሮች ሙሉ በሙሉ ለማግኘት ይረዳል።(ኢትዮ-መረጃ)
ጠቃሚ ነውና ለወዳጆ ያካፍሉ! ሼር!
Seledadotio
Seledadotio
Sponsored by
Surafel
19 days ago
የመጨረሻ አማራጬ ስለሆነ አንድ ነገር ከመሆኔ በፊት ግልፅ አድርጌ ልንገራችሁ። ለእናቴ ስል ነው ይሄን ለመፃፍ ሶሻል ሚዲያ ላይ የወጣሁት። የማያልፍ የለም አውቃለሁ ግን አንዴ ብታነቡት ነው። ይህ የእኔ ያለፉት ጥቂት አመታት አጭር ታሪክ ነው ለታሪክ ይቀመጥልኝ!!
የዛሬ አራት አመት አከባቢ እማዬን፤ እናትዬን ካንሰር አገኘብኝ። ያኔ እኔ 12ተኛ ክፍል ነበርኩ። 2015 ከገባበት ጊዜ ጀምሮ አመቱን ሙሉ ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ስትሰቃይ ነው የከረመችው። እኔም ከዛ በኋላ ፍፁም ሌላ ሰው ሆንኩ። በእኩለ ቀን አይኔን ሳልዘጋ ያቃዠኛል፤ መከራዋ ድንገት ድቅን ይልብኛል፤ ከሰዎች ጋር ቆሜ የሚታየኝ የሚሰማኝ ግን ሲቃ ነው ትምህርቱም አስጠላኝ ( btw I was really famous for my IQ and academic performance... እኔ ነበርኩ ማትሪክ ከፍተኛ ይሰራል ተብዬ ምጠበቀው) እናቴ ለኔ ትምህርት ራሷን ጥላ፤ እኔ በትምህርት ትልቅ ደረጃ ደርሼ ለማየት ሁሉ ነገሯን ሰውታ ቀርፃ ነው ያሳደገችኝ። የዘወትር የልጅነት ህልሜም አድጌ በሳይንሱ ዘርፍ ስኬታማ ሆኜ አሳይቻት የደስታና የተድላ ኑሮ ማኖር ነበር። 12ተኛ ክፍል ላይ ግን ሁሉም ነገር ተጠቅልሎ ገሃነም ገባብኝ። ስቃዩዋ እንደ ቁስል እየጠዘጠዘኝ እንኳን ላጠና ሌላ ነገር ማሰብ ራሱ አልቻልኩም (ድንገት ደንግጬ እነሳለሁ በለሊት... ስልክ እንዳልደውል ሰዓቱ በጣም ሄዷል)።
እንዲህ እንዲህ እየተባለ ማትሪክ ደርሶ ግቢ ገባን። ገና ከመግባቴ ከህንፃ ደረጃ ላይ ወድቄ ተሰባበርኩላችሁ። ሰው ፈተና ላይ እያለ እንደ እቃ በሽቦ ይጠግኑኛል😂 ካልተፈተንኩ ብዬ ቀወጥኩት ክሊኒኩ ውስጥ (እናቴ ከሰማች አውቃለሁ ምን እንደሚፈጠር) ግንኮ እግሬ በድን ሆኗል..ተሸክመው አስደግፈው አስተኙኝ። ሞላልቼ ተሸክመውኝ ይወጣሉ.. ሞላልቼ ተሸክመውኝ ይወጣሉ.. እያልን እያልን ፈተናው ልክ ሲያልቅ innovation ላይ እንድትሰሩ የተመረጣቹ ልጆች እዚሁ ቅሩ ሲባል አጋጣሚውን ተጠቅሜ እስክድን ግቢ ለመቆየት ወሰንኩ እሷ still ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ናት (I was in love with robotics btw)
ከሁለት ወር በኋላ እኔም ዳንኩ እሷም 'አሁን ደህና ስለሆነችና regular check up ህክምናዋን ከቤት እየመጣች በትክክል እስከተከታተለች ድረስ እስከ full life expectancy'ዋ መኖር ትችላለች "ድናለች"(it's not a fatal type of cancer if well-treated) ተብላ ቤት መጣች። በደስታ አበድን። "back to normal life somehow".. ከዛ ውጤትም መጣ (519)። I knew I had a bad year ግን still ተበሳጭቼ ነበር (የ highschool ego'ዬ ሙሉ በሙሉ አልጠፋም ነበር 😁)። ግቢ ገባሁ። ፍሬሽ year እግዚአብሔር ይመስገን በሰላም ጨረስኩ። 2nd year'ም ምንም አይልም ነበር። 3ተኛ አመት ላይ ግን ድጋሚ አመማት። traumaዬ እንዳለ መመለስ ጀመረ. እንቅልፍ እምቢ አለኝ... በዚያ ላይ the way the medical expenses hit us last time, ቃል የለኝም ታቁታላቹ የበሽታውን ባህሪይ (የደሟ ናሙና በየሁለት ወሩ ነው ውጪ ሚላከው).. እሱን እሱንም ሳስብ I knew we ain't gonna afford a single tablet this time!!!
በመጨረሻም አሁን ላይ እንደገና ደከማት። ደምም አንሷታል ብለው ደም ሰጥተው ቤት ላኳት። ከመጣች በኋላ ግን በጣም አመማት። ከአልጋ ላይ ራሱ ተነስታ መቆም አትችልም ከቀን ወደ ቀን ስቃይ ነው ምግብም ብዙ አይበላላትም ዶክተሩ ግን በቀጣይ ቀጠሮ ሰውነቷ ተመልሶ ማየት ፈልጋለሁ ብሏት ነበር። እንዲ ብሎ ከላካት በኋላ አሁን እንደዚ እንደደከማት አላየም። መድሃኒቱም አለቀ እስከ ቀጠሮው ቀን የምትውጠው። አሁኑኑ ዶክተር ካላያት እየተባለ ነው ግን we can't afford it right now! ቁጭ ብዬ ስቃዩዋን ማየት ከበደኝ 😭😭😭 የምሰራው video editing'ም በቂ ገንዘብ ሊያመጣልኝ አልቻለም። I can't lose her man I CAN'T!!!!! እማዬን አድኑልኝ!! ከማበዴ በፊት እናቴን አትርፉልኝ ዝም ብላቹ አትዩኝ PLEASE🙏🙏😭😭😭
በገንዘብ ካልቻላችሁ በፀሎታቹ አግዙኝ... It must mean something, right?? ለምታውቁት ሰው ሼር ብታረጉልኝ ባለውለታዎቼ ናችሁ!! እወዳችኋለሁ።
CBE: 1000558030759
የዛሬ አራት አመት አከባቢ እማዬን፤ እናትዬን ካንሰር አገኘብኝ። ያኔ እኔ 12ተኛ ክፍል ነበርኩ። 2015 ከገባበት ጊዜ ጀምሮ አመቱን ሙሉ ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ስትሰቃይ ነው የከረመችው። እኔም ከዛ በኋላ ፍፁም ሌላ ሰው ሆንኩ። በእኩለ ቀን አይኔን ሳልዘጋ ያቃዠኛል፤ መከራዋ ድንገት ድቅን ይልብኛል፤ ከሰዎች ጋር ቆሜ የሚታየኝ የሚሰማኝ ግን ሲቃ ነው ትምህርቱም አስጠላኝ ( btw I was really famous for my IQ and academic performance... እኔ ነበርኩ ማትሪክ ከፍተኛ ይሰራል ተብዬ ምጠበቀው) እናቴ ለኔ ትምህርት ራሷን ጥላ፤ እኔ በትምህርት ትልቅ ደረጃ ደርሼ ለማየት ሁሉ ነገሯን ሰውታ ቀርፃ ነው ያሳደገችኝ። የዘወትር የልጅነት ህልሜም አድጌ በሳይንሱ ዘርፍ ስኬታማ ሆኜ አሳይቻት የደስታና የተድላ ኑሮ ማኖር ነበር። 12ተኛ ክፍል ላይ ግን ሁሉም ነገር ተጠቅልሎ ገሃነም ገባብኝ። ስቃዩዋ እንደ ቁስል እየጠዘጠዘኝ እንኳን ላጠና ሌላ ነገር ማሰብ ራሱ አልቻልኩም (ድንገት ደንግጬ እነሳለሁ በለሊት... ስልክ እንዳልደውል ሰዓቱ በጣም ሄዷል)።
እንዲህ እንዲህ እየተባለ ማትሪክ ደርሶ ግቢ ገባን። ገና ከመግባቴ ከህንፃ ደረጃ ላይ ወድቄ ተሰባበርኩላችሁ። ሰው ፈተና ላይ እያለ እንደ እቃ በሽቦ ይጠግኑኛል😂 ካልተፈተንኩ ብዬ ቀወጥኩት ክሊኒኩ ውስጥ (እናቴ ከሰማች አውቃለሁ ምን እንደሚፈጠር) ግንኮ እግሬ በድን ሆኗል..ተሸክመው አስደግፈው አስተኙኝ። ሞላልቼ ተሸክመውኝ ይወጣሉ.. ሞላልቼ ተሸክመውኝ ይወጣሉ.. እያልን እያልን ፈተናው ልክ ሲያልቅ innovation ላይ እንድትሰሩ የተመረጣቹ ልጆች እዚሁ ቅሩ ሲባል አጋጣሚውን ተጠቅሜ እስክድን ግቢ ለመቆየት ወሰንኩ እሷ still ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ናት (I was in love with robotics btw)
ከሁለት ወር በኋላ እኔም ዳንኩ እሷም 'አሁን ደህና ስለሆነችና regular check up ህክምናዋን ከቤት እየመጣች በትክክል እስከተከታተለች ድረስ እስከ full life expectancy'ዋ መኖር ትችላለች "ድናለች"(it's not a fatal type of cancer if well-treated) ተብላ ቤት መጣች። በደስታ አበድን። "back to normal life somehow".. ከዛ ውጤትም መጣ (519)። I knew I had a bad year ግን still ተበሳጭቼ ነበር (የ highschool ego'ዬ ሙሉ በሙሉ አልጠፋም ነበር 😁)። ግቢ ገባሁ። ፍሬሽ year እግዚአብሔር ይመስገን በሰላም ጨረስኩ። 2nd year'ም ምንም አይልም ነበር። 3ተኛ አመት ላይ ግን ድጋሚ አመማት። traumaዬ እንዳለ መመለስ ጀመረ. እንቅልፍ እምቢ አለኝ... በዚያ ላይ the way the medical expenses hit us last time, ቃል የለኝም ታቁታላቹ የበሽታውን ባህሪይ (የደሟ ናሙና በየሁለት ወሩ ነው ውጪ ሚላከው).. እሱን እሱንም ሳስብ I knew we ain't gonna afford a single tablet this time!!!
በመጨረሻም አሁን ላይ እንደገና ደከማት። ደምም አንሷታል ብለው ደም ሰጥተው ቤት ላኳት። ከመጣች በኋላ ግን በጣም አመማት። ከአልጋ ላይ ራሱ ተነስታ መቆም አትችልም ከቀን ወደ ቀን ስቃይ ነው ምግብም ብዙ አይበላላትም ዶክተሩ ግን በቀጣይ ቀጠሮ ሰውነቷ ተመልሶ ማየት ፈልጋለሁ ብሏት ነበር። እንዲ ብሎ ከላካት በኋላ አሁን እንደዚ እንደደከማት አላየም። መድሃኒቱም አለቀ እስከ ቀጠሮው ቀን የምትውጠው። አሁኑኑ ዶክተር ካላያት እየተባለ ነው ግን we can't afford it right now! ቁጭ ብዬ ስቃዩዋን ማየት ከበደኝ 😭😭😭 የምሰራው video editing'ም በቂ ገንዘብ ሊያመጣልኝ አልቻለም። I can't lose her man I CAN'T!!!!! እማዬን አድኑልኝ!! ከማበዴ በፊት እናቴን አትርፉልኝ ዝም ብላቹ አትዩኝ PLEASE🙏🙏😭😭😭
በገንዘብ ካልቻላችሁ በፀሎታቹ አግዙኝ... It must mean something, right?? ለምታውቁት ሰው ሼር ብታረጉልኝ ባለውለታዎቼ ናችሁ!! እወዳችኋለሁ።
CBE: 1000558030759
19 days ago
610,000 ሺህ ሰዎች በወባ ይሞታሉ
* በዓለም 282 ሚሊዮን ሰዎች በወባ ተይዘዋል
#ethiopia | የአለም ጤና ድርጅት ምንም እንኳን በዓለም አቀፍ ደረጃ በወባ ተይዘው የሚሞቱ ሰዎች ቁጥር ቢቀንስም ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ግን በሽታውን በመከላከል እና በመቆጣጠር ረገድ እንቅፋቶች ተፈጥረዋል ብሏል።
ይህ ደግሞ ካለፈው ዓመት ጋር ሲነጻጸር በ598,000 ጭማሪ ያሳየ መሆኑን የዓለም ጤና ድርጅት መረጃ ያሳያል።
በአፍሪካ በርካቶቹ በበሽታው ተይዘው የሞቱት ሕጻናት መሆናቸው ድርጅቱ ገልጿል።
47 አገራት ከወባ ነጻ መሆናቸው ቢታወጅም ኢትዮጵያን ጨምሮ በማዳጋስካር አፍጋኒስታን እና የመን ደግሞ በበሽታው የተያዙ ሰዎች ቁጥር ጨምሯል።
የዓለም ጤና ድርጅት ለበሽታው መጨመር የአየር ንብረት ለውጥ አንዱ ምክንያት መሆኑን ያስቀምጣል።
የከባቢ አየር መሞቅ የወባ ትንኝ ምቹ የመራቢያ ስፍራ እንዲኖራት በማድረግ ከዚህ ቀደም ወዳልተጠቁ አካባቢዎች እንድትስፋፋ አግዟታል ይላሉ።
በሽታውን ለመከላከል ይደረግ የነበረው ዓለም አቀፍ ድጋፍ መቋረጥ ከዚህ ቀደም ወባን ይገድሉ የነበሩ መድሃኒቶችን የሚቋቋም ዝርያ መፈጠር የዓለም ጤና ድርጅት ከጠቀሳቸው ምክንያቶች መካከል ናቸው።
ባለሙያዎች የወባ ወደ አዳዳሲ አካባቢዎች መስፋፋት የመከላከል አቅም ያላዳበሩ ሕዝቦች ከባድ ለሆነ በሽታ እንዲጋለጡ ያደርጋል ሲሉ ስጋታቸውን ገልጸዋል።
ሔኖክ ወ/ገብርኤል
#ethiopia #getutemesgen #getunews #worldheathorganization #malariaafricahealth
* በዓለም 282 ሚሊዮን ሰዎች በወባ ተይዘዋል
#ethiopia | የአለም ጤና ድርጅት ምንም እንኳን በዓለም አቀፍ ደረጃ በወባ ተይዘው የሚሞቱ ሰዎች ቁጥር ቢቀንስም ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ግን በሽታውን በመከላከል እና በመቆጣጠር ረገድ እንቅፋቶች ተፈጥረዋል ብሏል።
ይህ ደግሞ ካለፈው ዓመት ጋር ሲነጻጸር በ598,000 ጭማሪ ያሳየ መሆኑን የዓለም ጤና ድርጅት መረጃ ያሳያል።
በአፍሪካ በርካቶቹ በበሽታው ተይዘው የሞቱት ሕጻናት መሆናቸው ድርጅቱ ገልጿል።
47 አገራት ከወባ ነጻ መሆናቸው ቢታወጅም ኢትዮጵያን ጨምሮ በማዳጋስካር አፍጋኒስታን እና የመን ደግሞ በበሽታው የተያዙ ሰዎች ቁጥር ጨምሯል።
የዓለም ጤና ድርጅት ለበሽታው መጨመር የአየር ንብረት ለውጥ አንዱ ምክንያት መሆኑን ያስቀምጣል።
የከባቢ አየር መሞቅ የወባ ትንኝ ምቹ የመራቢያ ስፍራ እንዲኖራት በማድረግ ከዚህ ቀደም ወዳልተጠቁ አካባቢዎች እንድትስፋፋ አግዟታል ይላሉ።
በሽታውን ለመከላከል ይደረግ የነበረው ዓለም አቀፍ ድጋፍ መቋረጥ ከዚህ ቀደም ወባን ይገድሉ የነበሩ መድሃኒቶችን የሚቋቋም ዝርያ መፈጠር የዓለም ጤና ድርጅት ከጠቀሳቸው ምክንያቶች መካከል ናቸው።
ባለሙያዎች የወባ ወደ አዳዳሲ አካባቢዎች መስፋፋት የመከላከል አቅም ያላዳበሩ ሕዝቦች ከባድ ለሆነ በሽታ እንዲጋለጡ ያደርጋል ሲሉ ስጋታቸውን ገልጸዋል።
ሔኖክ ወ/ገብርኤል
#ethiopia #getutemesgen #getunews #worldheathorganization #malariaafricahealth
20 days ago
በሀይቅ ላይ የሚጨመሩ ማዳበሪያዎችና ኬሚካሎች በዓሣ ተመጋቢዎች ዘንድ የጉበት በሽታ ስርጭት እንዲጨምር ማድረጋቸው ተነገረ
በሀራደምበል ሀይቅ ዙሪያ ከሚከናወኑ የግብርና መስኖ ስራዎች ጋር በተገናኘ የሚለቀቁ የናይትሬት እና ፎስፌት ማዳበሪያዎች እንዲሁም ከአካባቢዉ የአበባ እርሻዎች የሚወጡ ኬሚካሎች ሀይቁን እየበከሉት እንደሚገኙ የባቱ ከተማ ግብርና ፅህፈት ቤት ኃላፊ ዶክተር ለሚ ኮርሶ ከብስራት ሬዲዮ ጋር በነበራቸው ቆይታ ተናግረዋል ።
በእነዚህ ማዳበሪያዎችና ኬሚካሎች መበከል ምክኒያት በአካባቢው በሚገኙ የዓሣ ተመጋቢዎች ዘንድ የጉበት በሽታ ስርጭት እንዲጨምር ሆኗል::ከኬሚካሎች መበከል ጋር ተያይዞ በቅርቡ በተደረገ ምርመራ ከ4 ሺህ ሰዎች መካከል 400 ያህሎቹ ወይም 10 በመቶ የሚሆኑት በጉበት በሽታ መያዛቸው ተነግሯል።
ይህም በጉበት ላይ ትልቅ ችግር የሚያስከትል እና ዋነኛ ስጋት እየሆነ መምጣቱን የሚገልፁት የባቱ ከተማ ግብርና ፅህፈት ቤት ኃላፊ ዶክተር ለሚ ኮርሶ በሀይቁ ዙሪያ በመስኖ ስራ ላይ የተሠማሩ ግለሰቦች ማዳበሪያዎችን ወደ ሀይቅ ከመልቀቅ እንዲቆጠቡ አሳስበዋል ።እንዲሁም በአከባቢው የሚገኙ የአበባ እርሻዎችም ኬሚካሎችን ወደ ሀይቁ ከመልቀቅ መቆጠብ ይኖርባቸዋል ተብሏል ።
Seledadotio
Seledadotio
በሀራደምበል ሀይቅ ዙሪያ ከሚከናወኑ የግብርና መስኖ ስራዎች ጋር በተገናኘ የሚለቀቁ የናይትሬት እና ፎስፌት ማዳበሪያዎች እንዲሁም ከአካባቢዉ የአበባ እርሻዎች የሚወጡ ኬሚካሎች ሀይቁን እየበከሉት እንደሚገኙ የባቱ ከተማ ግብርና ፅህፈት ቤት ኃላፊ ዶክተር ለሚ ኮርሶ ከብስራት ሬዲዮ ጋር በነበራቸው ቆይታ ተናግረዋል ።
በእነዚህ ማዳበሪያዎችና ኬሚካሎች መበከል ምክኒያት በአካባቢው በሚገኙ የዓሣ ተመጋቢዎች ዘንድ የጉበት በሽታ ስርጭት እንዲጨምር ሆኗል::ከኬሚካሎች መበከል ጋር ተያይዞ በቅርቡ በተደረገ ምርመራ ከ4 ሺህ ሰዎች መካከል 400 ያህሎቹ ወይም 10 በመቶ የሚሆኑት በጉበት በሽታ መያዛቸው ተነግሯል።
ይህም በጉበት ላይ ትልቅ ችግር የሚያስከትል እና ዋነኛ ስጋት እየሆነ መምጣቱን የሚገልፁት የባቱ ከተማ ግብርና ፅህፈት ቤት ኃላፊ ዶክተር ለሚ ኮርሶ በሀይቁ ዙሪያ በመስኖ ስራ ላይ የተሠማሩ ግለሰቦች ማዳበሪያዎችን ወደ ሀይቅ ከመልቀቅ እንዲቆጠቡ አሳስበዋል ።እንዲሁም በአከባቢው የሚገኙ የአበባ እርሻዎችም ኬሚካሎችን ወደ ሀይቁ ከመልቀቅ መቆጠብ ይኖርባቸዋል ተብሏል ።
Seledadotio
Seledadotio
20 days ago
የኢትዮጵያን የግብርና ምርታማነት ለማሳደግ ያለመ አዲስ የቴክኖሎጂ አማራጭ ይፋ ተደረገ
#fastmereja I በኢትዮጵያ የግብርና ምርታማነትን ለማሳደግ፣ የወጪ ንግድ ጥራትን ለመጠበቅ እና የአርሶ አደሩን ድካም ለመቀነስ የሰው ሰራሽ አስተዋጽኦ (AI) ቴክኖሎጂዎችን፣ ዘመናዊ የካሜራ ቁጥጥሮችን እና የከርሰ ምድር ሴንሰሮችን ያካተቱ አዳዲስ የግብርና መፍትሄዎች ወደ አገር ውስጥ እየገቡ መሆኑ ታውቋል።
ጎልደን ላንድ ቶኩማ የተሰኘው የግብርና ቴክኖሎጂ ድርጅት በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ፣ የሰብል ጤንነትን መከታተል የሚያስችሉ ክሮፕለር የቴክኖሎጂ ውጤት ወደ ኢትዮጵያ የግብርና ስርዓት ለማስገባት ሰፊ ዝግጅት እየተደረገ እንደሚገኘ ተነግሯል። ይህ ቴክኖሎጂ በአገሪቱ እየተተገበረ ያለውን የዲጂታል ግብርና ፍኖተ ካርታ እውን ለማድረግ ትልቅ ሚና እንደሚጫወት ታምኖበታል።
በተለይ በአገሪቱ የወጪ ንግድ ላይ ትልቅ ድርሻ ላላቸው እንደ ቡና እና የአትክልትና ፍራፍሬ ምርቶች ላይ ትኩረት አድርጎ የሚሰራው ይህ አዲስ አሰራር፣ ሰብሎች ከመሬት ሳይነቀሉ በካሜራ እና በሳተላይት ድጋፍ በሽታዎችን ቀድሞ ለመለየት ያስችላል። ሰብሎችን በአካል የመጎብኘትና የመቆጣጠር ወጪን እስከ 40 በመቶ እንደሚቀንስ የተረጋገጠ ሲሆን፣ አርሶ አደሮችና ባለሀብቶች የተሻለ የውሳኔ አሰጣጥ ብቃት እንዲኖራቸው ይረዳል ተብሏል።
ይህ የቴክኖሎጂ መፍትሄ በአሁኑ ወቅት በዓለም አቀፍ ደረጃ ከ22 በላይ አገራት ውስጥ ጥቅም ላይ የዋለ ሲሆን፣ በኢትዮጵያ ደግሞ በዋናነት ለትላልቅና መካከለኛ የንግድ እርሻዎች፣ ለቡና ላኪዎች፣ ለአግሮ-ኢንደስትሪዎች እና በተደራጁ የህብረት ስራ ማህበራት ስር ለሚገኙ አርሶ አደሮች ሰፊ ጠቀሜታ እንደሚሰጥ ይጠበቃል።
#fastmereja I በኢትዮጵያ የግብርና ምርታማነትን ለማሳደግ፣ የወጪ ንግድ ጥራትን ለመጠበቅ እና የአርሶ አደሩን ድካም ለመቀነስ የሰው ሰራሽ አስተዋጽኦ (AI) ቴክኖሎጂዎችን፣ ዘመናዊ የካሜራ ቁጥጥሮችን እና የከርሰ ምድር ሴንሰሮችን ያካተቱ አዳዲስ የግብርና መፍትሄዎች ወደ አገር ውስጥ እየገቡ መሆኑ ታውቋል።
ጎልደን ላንድ ቶኩማ የተሰኘው የግብርና ቴክኖሎጂ ድርጅት በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ፣ የሰብል ጤንነትን መከታተል የሚያስችሉ ክሮፕለር የቴክኖሎጂ ውጤት ወደ ኢትዮጵያ የግብርና ስርዓት ለማስገባት ሰፊ ዝግጅት እየተደረገ እንደሚገኘ ተነግሯል። ይህ ቴክኖሎጂ በአገሪቱ እየተተገበረ ያለውን የዲጂታል ግብርና ፍኖተ ካርታ እውን ለማድረግ ትልቅ ሚና እንደሚጫወት ታምኖበታል።
በተለይ በአገሪቱ የወጪ ንግድ ላይ ትልቅ ድርሻ ላላቸው እንደ ቡና እና የአትክልትና ፍራፍሬ ምርቶች ላይ ትኩረት አድርጎ የሚሰራው ይህ አዲስ አሰራር፣ ሰብሎች ከመሬት ሳይነቀሉ በካሜራ እና በሳተላይት ድጋፍ በሽታዎችን ቀድሞ ለመለየት ያስችላል። ሰብሎችን በአካል የመጎብኘትና የመቆጣጠር ወጪን እስከ 40 በመቶ እንደሚቀንስ የተረጋገጠ ሲሆን፣ አርሶ አደሮችና ባለሀብቶች የተሻለ የውሳኔ አሰጣጥ ብቃት እንዲኖራቸው ይረዳል ተብሏል።
ይህ የቴክኖሎጂ መፍትሄ በአሁኑ ወቅት በዓለም አቀፍ ደረጃ ከ22 በላይ አገራት ውስጥ ጥቅም ላይ የዋለ ሲሆን፣ በኢትዮጵያ ደግሞ በዋናነት ለትላልቅና መካከለኛ የንግድ እርሻዎች፣ ለቡና ላኪዎች፣ ለአግሮ-ኢንደስትሪዎች እና በተደራጁ የህብረት ስራ ማህበራት ስር ለሚገኙ አርሶ አደሮች ሰፊ ጠቀሜታ እንደሚሰጥ ይጠበቃል።
21 days ago
በቀን 3 ቴምር መብላት ለአእምሮ ጥንካሬና ከአልዛይመር ለመከላከል ፍቱን መፍትሔ _ጥናት
በሎማ ሊንዳ ዩኒቨርሲቲ (ካሊፎርኒያ፣ አሜሪካ) ተመራማሪዎች የተጠናና በቅርቡ ‘ጆርናል ኦፍ ኒውትሪሽን’ ላይ የታተመ ጥናት እንደሚያመለክተው በቀን ሦስት ቴምር መመገብ ለአእምሮ ጤና ከፍተኛ ጠቀሜታ ያለው ከመሆኑም በላይ የትርሳን (የአልዛይመር) በሽታ የመያዝ ተጋላጭነትን በእጅጉ ይቀንሳል።
ቴምር የአእምሮ ሴሎችን ከጉዳት የሚጠብቁና እብጠትን የሚከላከሉ እንደ ፍላቮኖይድስ እና ፌኖሊክ አሲድ ያሉ አንቲኦክሲዳንቶች እንዲሁም በርካታ ጠቃሚ ቪታሚኖች በውስጡ ይዟል።
በሳይንሳዊ ምርምሮች መሠረት፣ ቴምር በአእምሮ ውስጥ የሚፈጠሩትንና ለአልዛይመር በሽታ መከሰት ዋነኛ መንስኤ የሆኑትን የ"አሚሎይድ ፕላኮች" (amyloid plaques) ክምችት የመከላከል ከፍተኛ አቅም አለው።
ሆኖም ግን ቴምር ከፍተኛ የካሎሪና የስኳር መጠን ስላለው (በ100 ግራም ውስጥ ወደ 66 ግራም ስኳር ይገኛል)፣ በተለይ የስኳር ህመምተኞች እና የጨጓራ ወይም የአንጀት ችግር ያለባቸው ሰዎች በሚመገቡበት ጊዜ መጠን ማወቅና ተገቢውን ጥንቃቄ ማድረግ እንዳለባቸው ምሁራን ያሳስባሉ።
Seledadotio
Seledadotio
በሎማ ሊንዳ ዩኒቨርሲቲ (ካሊፎርኒያ፣ አሜሪካ) ተመራማሪዎች የተጠናና በቅርቡ ‘ጆርናል ኦፍ ኒውትሪሽን’ ላይ የታተመ ጥናት እንደሚያመለክተው በቀን ሦስት ቴምር መመገብ ለአእምሮ ጤና ከፍተኛ ጠቀሜታ ያለው ከመሆኑም በላይ የትርሳን (የአልዛይመር) በሽታ የመያዝ ተጋላጭነትን በእጅጉ ይቀንሳል።
ቴምር የአእምሮ ሴሎችን ከጉዳት የሚጠብቁና እብጠትን የሚከላከሉ እንደ ፍላቮኖይድስ እና ፌኖሊክ አሲድ ያሉ አንቲኦክሲዳንቶች እንዲሁም በርካታ ጠቃሚ ቪታሚኖች በውስጡ ይዟል።
በሳይንሳዊ ምርምሮች መሠረት፣ ቴምር በአእምሮ ውስጥ የሚፈጠሩትንና ለአልዛይመር በሽታ መከሰት ዋነኛ መንስኤ የሆኑትን የ"አሚሎይድ ፕላኮች" (amyloid plaques) ክምችት የመከላከል ከፍተኛ አቅም አለው።
ሆኖም ግን ቴምር ከፍተኛ የካሎሪና የስኳር መጠን ስላለው (በ100 ግራም ውስጥ ወደ 66 ግራም ስኳር ይገኛል)፣ በተለይ የስኳር ህመምተኞች እና የጨጓራ ወይም የአንጀት ችግር ያለባቸው ሰዎች በሚመገቡበት ጊዜ መጠን ማወቅና ተገቢውን ጥንቃቄ ማድረግ እንዳለባቸው ምሁራን ያሳስባሉ።
Seledadotio
Seledadotio
21 days ago
የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት 100ኛ ዓመቱን አከበረ
#ethiopia | የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት (EPHI) "የአንድ ክፍለ ዘመን ጥረት ለተሻለ የሕብረተሰብ ጤና" በሚል መሪ ቃል ታሪካዊ የ100ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን ዛሬ በከፍተኛ ድምቀት አክብሯል።
ይህ መቶ ዓመታትን የተሻገረው ክብረ በዓል ተቋሙ ላለፉት አሥርት ዓመታት የሀገሪቱን የጤና ደህንነት ለመጠበቅ ያደረገውን ዘርፈ ብዙ ጉዞ የዘከረ ሲሆን፣ በቀጣይም የጤና ሥርዓቱን ወደ ላቀ ምዕራፍ ለማሸጋገር አዲስ ቃል ኪዳን የተገባበት መድረክ ሆኗል።
በበዓሉ ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ክቡር ታዬ አፅቀስላሴ ጠንካራ የሕብረተሰብ ጤና ተቋማት የሀገር ደህንነትና ልማት መሠረቶች መሆናቸውን በመግለጽ፣ መንግሥት ተቋሙን ይበልጥ ለማጠናከር ቅድሚያ ሰጥቶ እንደሚሠራ አረጋግጠዋል።
ፕሬዚዳንቱ አክለውም ተቋሙ ከጊዜው ጋር እንዲራመድ የዲጂታል ቴክኖሎጂንና የሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) አጠቃቀምን ማሳደግ እንደሚገባው አሳስበዋል።
በተመሳሳይ መልኩ የጤና ሚኒስትሯ ክብርት ዶክተር መቅደስ ዳባ ተቋሙ ላለፉት 100 ዓመታት በበሽታ ቅኝት፣ በላቦራቶሪ አገልግሎትና በምርምር ዘርፍ ያበረከተውን ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያወሱ ሲሆን፣ አዳዲስ ወረርሽኞችንና የአየር ንብረት ለውጥ ያመጣቸውን የጤና ተግዳሮቶች ለመመከት ጠንካራ ተቋማዊ ትብብር እንደሚያስፈልግ በአፅንኦት ገልጸዋል።
የዓለም ጤና ድርጅት (WHO) በኢትዮጵያ ተወካይ ፕሮፌሰር ፍራንሲስ ካስሎ በበኩላቸው ኢንስቲትዩቱ በአፍሪካ እጅግ ጠንካራ ከሆኑ የልህቀት ማዕከላት አንዱ መሆኑን ጠቅሰው፣ ተቋሙን የዓለም ጤና ድርጅት የትብብር ማዕከል ለማድረግ እንቅስቃሴ መጀመሩን ይፋ አድርገዋል።
የአፍሪካ የበሽታ መከላከያና መቆጣጠሪያ ማዕከል (Africa CDC) ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ጄን ካሴያም በበኩላቸው የወደፊቱ የሕብረተሰብ ጤና ያለ ሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) የማይታሰብ መሆኑን ጠቁመው፣ ኢትዮጵያ በዚህ ረገድ እያደረገች ያለችው ጥረት ለጤናው ዘርፍ ስኬት ትልቅ አቅም እንደሚፈጥር ገልጸዋል።
የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር ዶክተር መሳይ ኃይሉ ተቋሙ ያለፉትን ስኬቶች መሠረት በማድረግ በቀጣዩ መቶ ዓመታት የሀገሪቱን የሳይንስና የጤና ሉዓላዊነት በተሟላ ሁኔታ ለማረጋገጥ በቁርጠኝነት እንደሚሠራ ቃል ገብተዋል።
በበዓሉ ማጠቃለያ ላይም ላለፉት ዓመታት ተቋሙን በምርምርና በአመራርነት ያገለገሉ ባለውለታዎች ከፕሬዚዳንት ታዬ አፅቀስላሴ እጅ የእውቅና ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።
ጌትነት ተመስገን
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
#healthsovereignty #publichealthethiopia
#aiinhealthcare #ethiopia
#ephi #ministryofhealthethiopia
#ethiopia | የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት (EPHI) "የአንድ ክፍለ ዘመን ጥረት ለተሻለ የሕብረተሰብ ጤና" በሚል መሪ ቃል ታሪካዊ የ100ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን ዛሬ በከፍተኛ ድምቀት አክብሯል።
ይህ መቶ ዓመታትን የተሻገረው ክብረ በዓል ተቋሙ ላለፉት አሥርት ዓመታት የሀገሪቱን የጤና ደህንነት ለመጠበቅ ያደረገውን ዘርፈ ብዙ ጉዞ የዘከረ ሲሆን፣ በቀጣይም የጤና ሥርዓቱን ወደ ላቀ ምዕራፍ ለማሸጋገር አዲስ ቃል ኪዳን የተገባበት መድረክ ሆኗል።
በበዓሉ ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ክቡር ታዬ አፅቀስላሴ ጠንካራ የሕብረተሰብ ጤና ተቋማት የሀገር ደህንነትና ልማት መሠረቶች መሆናቸውን በመግለጽ፣ መንግሥት ተቋሙን ይበልጥ ለማጠናከር ቅድሚያ ሰጥቶ እንደሚሠራ አረጋግጠዋል።
ፕሬዚዳንቱ አክለውም ተቋሙ ከጊዜው ጋር እንዲራመድ የዲጂታል ቴክኖሎጂንና የሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) አጠቃቀምን ማሳደግ እንደሚገባው አሳስበዋል።
በተመሳሳይ መልኩ የጤና ሚኒስትሯ ክብርት ዶክተር መቅደስ ዳባ ተቋሙ ላለፉት 100 ዓመታት በበሽታ ቅኝት፣ በላቦራቶሪ አገልግሎትና በምርምር ዘርፍ ያበረከተውን ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያወሱ ሲሆን፣ አዳዲስ ወረርሽኞችንና የአየር ንብረት ለውጥ ያመጣቸውን የጤና ተግዳሮቶች ለመመከት ጠንካራ ተቋማዊ ትብብር እንደሚያስፈልግ በአፅንኦት ገልጸዋል።
የዓለም ጤና ድርጅት (WHO) በኢትዮጵያ ተወካይ ፕሮፌሰር ፍራንሲስ ካስሎ በበኩላቸው ኢንስቲትዩቱ በአፍሪካ እጅግ ጠንካራ ከሆኑ የልህቀት ማዕከላት አንዱ መሆኑን ጠቅሰው፣ ተቋሙን የዓለም ጤና ድርጅት የትብብር ማዕከል ለማድረግ እንቅስቃሴ መጀመሩን ይፋ አድርገዋል።
የአፍሪካ የበሽታ መከላከያና መቆጣጠሪያ ማዕከል (Africa CDC) ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ጄን ካሴያም በበኩላቸው የወደፊቱ የሕብረተሰብ ጤና ያለ ሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) የማይታሰብ መሆኑን ጠቁመው፣ ኢትዮጵያ በዚህ ረገድ እያደረገች ያለችው ጥረት ለጤናው ዘርፍ ስኬት ትልቅ አቅም እንደሚፈጥር ገልጸዋል።
የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር ዶክተር መሳይ ኃይሉ ተቋሙ ያለፉትን ስኬቶች መሠረት በማድረግ በቀጣዩ መቶ ዓመታት የሀገሪቱን የሳይንስና የጤና ሉዓላዊነት በተሟላ ሁኔታ ለማረጋገጥ በቁርጠኝነት እንደሚሠራ ቃል ገብተዋል።
በበዓሉ ማጠቃለያ ላይም ላለፉት ዓመታት ተቋሙን በምርምርና በአመራርነት ያገለገሉ ባለውለታዎች ከፕሬዚዳንት ታዬ አፅቀስላሴ እጅ የእውቅና ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።
ጌትነት ተመስገን
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
#healthsovereignty #publichealthethiopia
#aiinhealthcare #ethiopia
#ephi #ministryofhealthethiopia
23 days ago
ሰውሰራሽ አስተውሎት፡ የግብርናው አዲስ አጋር
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 7፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ኢትዮጵያ በግብርና ላይ የተመሠረተ ኢኮኖሚ ያላት ሀገር መሆኗ የሚታወቅ ነው። በሚሊየኖች የሚቆጠሩ ዜጎች ኑሯቸውን የሚመሩት በእርሻ ነው።
ሆኖም የአየር ንብረት ለውጥ፣ የተባይ መስፋፋት፣ የገበያ አለመረጋጋት እና የመረጃ እጥረት ዘርፉን አሁንም በፈተና ውስጥ አድርገውታል።
በዚህ መካከል ግን የሰው ሠራሽ አስተውሎት አዲስ ተስፋ ይዞ ብቅ ብሏል።
አንዳንዶች ሰው ሰራሽ አስተውሎትን የሮቦቶች ዓለም እንደሆነ ያስባሉ፤ እውነታው ግን የግብርናን ሥራ ቀላል፣ ፈጣን እና ውጤታማ የሚያደርግ ውጤታማ የመረጃ ሥርዓት ነው።
ሰውሰራሽ አስተውሎት የሰውን ጉልበት የሚተካ ሳይሆን የሚያጠናክር ቴክኖሎጂ ነው።
ይህ ቴክኖሎጂ ለኢትዮጵያ ደግሞ የግብርና ምርታማነትን ለማሳደግ፣ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ እና የሀገሪቱን ኢኮኖሚ ወደ አዲስ ምዕራፍ ለማሸጋገር ትልቅ እድል ይዞ መጥቷል።
ሰው ሰራሽ አስተውሎት የአየር ሁኔታ መረጃዎችን በመተንተን የዝናብ፣ የድርቅና የሙቀት ለውጦችን አስቀድሞ መተንበይ ይችላል።
ይህም አርሶ አደሮች መቼ እንደሚዘሩ፣ መቼ እንደሚሰበስቡ እና እንዴት ምርታቸውን እንደሚጠብቁ በትክክል እንዲወስኑ ያግዛል።
በሌላ በኩል ቀደም ሲል የእጽዋት በሽታዎችን እና ተባዮችን ለመለየት የግብርና ባለሙያ መጠበቅ ግድ ይል ነበር። ዛሬ ግን በሞባይል ስልክ በተነሳ ፎቶ ብቻ በቴክኖሎጂው በመታገዝ በጥቂት ሰከንዶች ውስጥ በሽታውን መለየት የሚቻልበት ሁኔታ ተፈጥሯል።
ይህም ተባዮችና በሽታዎች ከመስፋፋታቸው በፊት ፈጣን ርምጃ እንዲወሰድ እገዛ ያደርጋል።
በተጨማሪም ከአፈር ሴንሰሮች የሚሰበስበውን መረጃ በመተንተን ቴክኖሎጂው እፅዋት መቼ ውሃ እንደሚፈልጉ መረጃ በመስጠት የውሃ ብክነት እና ወጪን ይቀንሳል።
የኢትዮጵያ በግብርናው ዘርፍ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ በመጠቀም ረገድ በለውጡ ዓመታት በርካታ ተግባራትን አከናውናለች።
ለአብነትም የሰብል እድገትን፣ የምርት መጠንን እና የድርቅ አደጋን ለመገምገም፤ እንደ አንበጣ ያሉ ተባዮችን አስቀድሞ መለየትና ፈጣን ምላሽ መስጠት፤ ለአርሶ አደሮች ስለ አየር ሁኔታ፣ የመዝራት ጊዜ፣ የማዳበሪያ አጠቃቀም እና የሰብል እንክብካቤ መረጃ በዲጂታል መንገድ ማቅረብ ይጠቀሳሉ።
ብዙ የግብርና መረጃዎችን በመተንተን ለፖሊሲ አውጪዎች እና ለውሳኔ ሰጪዎች ትክክለኛ የውሳኔ ድጋፍ መስጠት፣ ግብርናን ለማዘመን፣ የምርት መጠንን ለማሳደግ እና የምግብ ዋስትናን ለማጠናከር በብሔራዊ የሰውሰራሽ አስተውሎት ስትራቴጂ ውስጥ ቅድሚያ ሰጥታለች።
ኢትዮጵያ ሰውሰራሽ አስተውሎትን በግብርናው ዘርፍ በመጠቀም የሰብል ምርታማነትን ለማሳደግ፣ የተፈጥሮ አደጋዎችን ለመቀነስ እና ለአርሶ አደሮች በመረጃ ላይ የተመሠረተ የግብርና አገልግሎት ለማቅረብ እየሰራችበት ትገኛለች፡፡
ሆኖም ግን ሰው ሰራሽ አስተውሎትን በብቃት ለመጠቀም ያስችል ዘንድ ፈጣን የኢንተርኔት አገልግሎት፣ የዲጂታል ክህሎት፣ የመረጃ ጥራት እና የቴክኖሎጂ መሠረተ ልማት መጠናከር ያስፈልጋል።
በተጨማሪም የግብርናው ስራ በሰውሰራሽ አስተውሎት በመታገዝ ይበልጥ ውጤታማ እንዲሆን ወጣቶች፣ የትምህርት ተቋማት፣ የግል ድርጅቶች እና መንግሥት እንዲሁም ሌሎች አካላት በጋራ እና በቅንጅት ሲሠሩ ይገባል።
በአመለወርቅ ደምሰው
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 7፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ኢትዮጵያ በግብርና ላይ የተመሠረተ ኢኮኖሚ ያላት ሀገር መሆኗ የሚታወቅ ነው። በሚሊየኖች የሚቆጠሩ ዜጎች ኑሯቸውን የሚመሩት በእርሻ ነው።
ሆኖም የአየር ንብረት ለውጥ፣ የተባይ መስፋፋት፣ የገበያ አለመረጋጋት እና የመረጃ እጥረት ዘርፉን አሁንም በፈተና ውስጥ አድርገውታል።
በዚህ መካከል ግን የሰው ሠራሽ አስተውሎት አዲስ ተስፋ ይዞ ብቅ ብሏል።
አንዳንዶች ሰው ሰራሽ አስተውሎትን የሮቦቶች ዓለም እንደሆነ ያስባሉ፤ እውነታው ግን የግብርናን ሥራ ቀላል፣ ፈጣን እና ውጤታማ የሚያደርግ ውጤታማ የመረጃ ሥርዓት ነው።
ሰውሰራሽ አስተውሎት የሰውን ጉልበት የሚተካ ሳይሆን የሚያጠናክር ቴክኖሎጂ ነው።
ይህ ቴክኖሎጂ ለኢትዮጵያ ደግሞ የግብርና ምርታማነትን ለማሳደግ፣ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ እና የሀገሪቱን ኢኮኖሚ ወደ አዲስ ምዕራፍ ለማሸጋገር ትልቅ እድል ይዞ መጥቷል።
ሰው ሰራሽ አስተውሎት የአየር ሁኔታ መረጃዎችን በመተንተን የዝናብ፣ የድርቅና የሙቀት ለውጦችን አስቀድሞ መተንበይ ይችላል።
ይህም አርሶ አደሮች መቼ እንደሚዘሩ፣ መቼ እንደሚሰበስቡ እና እንዴት ምርታቸውን እንደሚጠብቁ በትክክል እንዲወስኑ ያግዛል።
በሌላ በኩል ቀደም ሲል የእጽዋት በሽታዎችን እና ተባዮችን ለመለየት የግብርና ባለሙያ መጠበቅ ግድ ይል ነበር። ዛሬ ግን በሞባይል ስልክ በተነሳ ፎቶ ብቻ በቴክኖሎጂው በመታገዝ በጥቂት ሰከንዶች ውስጥ በሽታውን መለየት የሚቻልበት ሁኔታ ተፈጥሯል።
ይህም ተባዮችና በሽታዎች ከመስፋፋታቸው በፊት ፈጣን ርምጃ እንዲወሰድ እገዛ ያደርጋል።
በተጨማሪም ከአፈር ሴንሰሮች የሚሰበስበውን መረጃ በመተንተን ቴክኖሎጂው እፅዋት መቼ ውሃ እንደሚፈልጉ መረጃ በመስጠት የውሃ ብክነት እና ወጪን ይቀንሳል።
የኢትዮጵያ በግብርናው ዘርፍ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ በመጠቀም ረገድ በለውጡ ዓመታት በርካታ ተግባራትን አከናውናለች።
ለአብነትም የሰብል እድገትን፣ የምርት መጠንን እና የድርቅ አደጋን ለመገምገም፤ እንደ አንበጣ ያሉ ተባዮችን አስቀድሞ መለየትና ፈጣን ምላሽ መስጠት፤ ለአርሶ አደሮች ስለ አየር ሁኔታ፣ የመዝራት ጊዜ፣ የማዳበሪያ አጠቃቀም እና የሰብል እንክብካቤ መረጃ በዲጂታል መንገድ ማቅረብ ይጠቀሳሉ።
ብዙ የግብርና መረጃዎችን በመተንተን ለፖሊሲ አውጪዎች እና ለውሳኔ ሰጪዎች ትክክለኛ የውሳኔ ድጋፍ መስጠት፣ ግብርናን ለማዘመን፣ የምርት መጠንን ለማሳደግ እና የምግብ ዋስትናን ለማጠናከር በብሔራዊ የሰውሰራሽ አስተውሎት ስትራቴጂ ውስጥ ቅድሚያ ሰጥታለች።
ኢትዮጵያ ሰውሰራሽ አስተውሎትን በግብርናው ዘርፍ በመጠቀም የሰብል ምርታማነትን ለማሳደግ፣ የተፈጥሮ አደጋዎችን ለመቀነስ እና ለአርሶ አደሮች በመረጃ ላይ የተመሠረተ የግብርና አገልግሎት ለማቅረብ እየሰራችበት ትገኛለች፡፡
ሆኖም ግን ሰው ሰራሽ አስተውሎትን በብቃት ለመጠቀም ያስችል ዘንድ ፈጣን የኢንተርኔት አገልግሎት፣ የዲጂታል ክህሎት፣ የመረጃ ጥራት እና የቴክኖሎጂ መሠረተ ልማት መጠናከር ያስፈልጋል።
በተጨማሪም የግብርናው ስራ በሰውሰራሽ አስተውሎት በመታገዝ ይበልጥ ውጤታማ እንዲሆን ወጣቶች፣ የትምህርት ተቋማት፣ የግል ድርጅቶች እና መንግሥት እንዲሁም ሌሎች አካላት በጋራ እና በቅንጅት ሲሠሩ ይገባል።
በአመለወርቅ ደምሰው
Sponsored by
Surafel
25 days ago
#ጤናመረጃ 🍋
10 አስገራሚ የሎሚ የጤና ጥቅሞች!
ሎሚን🍋 አዘውትሮ መጠቀም ከሚያስገኛቸው
ጥቅሞች ዋና ዋናዎቹን አጠር አድርገን እንያለን።
1) በሽታ የመከላከል አቅምን ያሳድጋል፤ በቪታሚን ሲ የበለፀገ በመሆኑ ከጉንፋንና ከተለያዩ ተላላፊ ቫይረሶች ይከላከላል።
2) ለምግብ መፈጨት ሥርዓት፤ ጠዋት በለጋ ውሃ መጠጣት በጉበት ውስጥ ያሉ መርዛማ ነገሮችን ለማስወገድና አንጀትን ለማረጋጋት ይረዳል።
3) የቆዳን ውበት ይጠብቃል፤ የኮላጅን ምርትን በማፋጠን የቆዳ መሸብሸብን ይከላከላል፤ መልክን ያጠራል።
4) የኩላሊት ጠጠርን ይከላከላል፤ በውስጡ ያለው ሲትሪክ አሲድ የካልሲየም ጠጠር እንዳይፈጠርና በሽንት እንዲወገድ ያደርጋል።
5) የደም ማነስን ይከላከላል፤ ሰውነታችን ከምግብ የሚያገኘውን የብረት (Iron) ንጥረ ነገር በቀላሉ እንዲመጥ ያግዛል።
6) ለአፍ ጠረን መፍትሔ ነው፤ በአፍ ውስጥ ያሉ ባክቴሪያዎችን በማጥፋት ጠረንን ያድሳል፤ የጥርስ ሕመምንም ያስታግሳል።
7) ክብደትን ለመቀነስ ያግዛል፤ በውስጡ ያለው የፔክቲን ፋይበር የረሃብ ስሜትን የሚቀንስና ስብን ለማቃጠል የሚረዳ ነው።
8) የልብን ጤንነት ይጠብቃል፤ መጥፎ ኮሌስትሮልን በመቀነስ ለልብ ሕመም እና ለድንገተኛ ስትሮክ የመጋለጥ ዕድልን ያጠባል።
9) ካንሰርን ይከላከላል፤ በውስጡ ያሉ ተፈጥሯዊ ውህዶች (Flavonoids) የካንሰር ሴሎች እንዳይፈጠሩና እንዳይስፋፉ ይረዳሉ።
10) የደም ግፊትን ያስተካክላል፤ በውስጡ የሚገኘው ፖታሲየም የደም ስሮችን በማዝናናት የደም ግፊት ጤናማ እንዲሆን ያደርጋል።
ጠቃሚ ነውና ለወዳጆ ያካፍሉ! ሼር!
Seledadotio
Seledadotio
10 አስገራሚ የሎሚ የጤና ጥቅሞች!
ሎሚን🍋 አዘውትሮ መጠቀም ከሚያስገኛቸው
ጥቅሞች ዋና ዋናዎቹን አጠር አድርገን እንያለን።
1) በሽታ የመከላከል አቅምን ያሳድጋል፤ በቪታሚን ሲ የበለፀገ በመሆኑ ከጉንፋንና ከተለያዩ ተላላፊ ቫይረሶች ይከላከላል።
2) ለምግብ መፈጨት ሥርዓት፤ ጠዋት በለጋ ውሃ መጠጣት በጉበት ውስጥ ያሉ መርዛማ ነገሮችን ለማስወገድና አንጀትን ለማረጋጋት ይረዳል።
3) የቆዳን ውበት ይጠብቃል፤ የኮላጅን ምርትን በማፋጠን የቆዳ መሸብሸብን ይከላከላል፤ መልክን ያጠራል።
4) የኩላሊት ጠጠርን ይከላከላል፤ በውስጡ ያለው ሲትሪክ አሲድ የካልሲየም ጠጠር እንዳይፈጠርና በሽንት እንዲወገድ ያደርጋል።
5) የደም ማነስን ይከላከላል፤ ሰውነታችን ከምግብ የሚያገኘውን የብረት (Iron) ንጥረ ነገር በቀላሉ እንዲመጥ ያግዛል።
6) ለአፍ ጠረን መፍትሔ ነው፤ በአፍ ውስጥ ያሉ ባክቴሪያዎችን በማጥፋት ጠረንን ያድሳል፤ የጥርስ ሕመምንም ያስታግሳል።
7) ክብደትን ለመቀነስ ያግዛል፤ በውስጡ ያለው የፔክቲን ፋይበር የረሃብ ስሜትን የሚቀንስና ስብን ለማቃጠል የሚረዳ ነው።
8) የልብን ጤንነት ይጠብቃል፤ መጥፎ ኮሌስትሮልን በመቀነስ ለልብ ሕመም እና ለድንገተኛ ስትሮክ የመጋለጥ ዕድልን ያጠባል።
9) ካንሰርን ይከላከላል፤ በውስጡ ያሉ ተፈጥሯዊ ውህዶች (Flavonoids) የካንሰር ሴሎች እንዳይፈጠሩና እንዳይስፋፉ ይረዳሉ።
10) የደም ግፊትን ያስተካክላል፤ በውስጡ የሚገኘው ፖታሲየም የደም ስሮችን በማዝናናት የደም ግፊት ጤናማ እንዲሆን ያደርጋል።
ጠቃሚ ነውና ለወዳጆ ያካፍሉ! ሼር!
Seledadotio
Seledadotio
26 days ago
የማይሞተው ብቸኛው የምድር ፍጡር
እርጅናን በመቀልበስ የሕይወት ዑደቱን ወደ ሕፃንነት በመመለስ ለዘላለም መኖር የሚችል “የማይሞት” አስገራሚ ፍጡር በባሕር ጥልቀት ውስጥ መገኘቱ ዓለም አቀፍ ሳይንቲስቶችን አስደምሟል።
“ቱሪቶፕሲስ ዶርኒ” (Turritopsis dohrnii) የተባለውና በጣም አነስተኛ መጠን ያለው ይህ የጄሊፊሽ (Jellyfish) ዝርያ በሕይወት ዘመኑ ላይ አደጋ፣ በሽታ ወይም እርጅና ሲደቅንበት የራሱን ሴሎች ሙሉ በሙሉ በማደስ ወደ መጀመሪያው የፅንስ (Polyp) ደረጃ የመመለስ አስደናቂ የተፈጥሮ ብቃት አለው።
ይህ ማለት ፍጡሩ ሲያረጅ ከመሞት ይልቅ ልክ እንደገና ተወልዶ ወደ ሕፃንነቱ ይመለሳል፤ ይህንን ሂደት ደግሞ ሳይሞት ለዘላለም ደጋግሞ ማከናወን ይችላል።
ተመራማሪዎች የዚህን ፍጡር የዲኤንኤ (DNA) ምስጢር ለመፍታት ሌሊትና ቀን እየሠሩ የሚገኙ ሲሆን፣ ግኝቱ ለሰው ልጅ የእርጅና መከላከያ እና የካንሰር ሕክምና ምርምር ትልቅ ተስፋን የፈነጠቀ በመሆኑ በማኅበራዊ ሚዲያና በሳይንሱ ዓለም ከፍተኛ መነጋገሪያ ሆኗል።
Seledadotio
Seledadotio
እርጅናን በመቀልበስ የሕይወት ዑደቱን ወደ ሕፃንነት በመመለስ ለዘላለም መኖር የሚችል “የማይሞት” አስገራሚ ፍጡር በባሕር ጥልቀት ውስጥ መገኘቱ ዓለም አቀፍ ሳይንቲስቶችን አስደምሟል።
“ቱሪቶፕሲስ ዶርኒ” (Turritopsis dohrnii) የተባለውና በጣም አነስተኛ መጠን ያለው ይህ የጄሊፊሽ (Jellyfish) ዝርያ በሕይወት ዘመኑ ላይ አደጋ፣ በሽታ ወይም እርጅና ሲደቅንበት የራሱን ሴሎች ሙሉ በሙሉ በማደስ ወደ መጀመሪያው የፅንስ (Polyp) ደረጃ የመመለስ አስደናቂ የተፈጥሮ ብቃት አለው።
ይህ ማለት ፍጡሩ ሲያረጅ ከመሞት ይልቅ ልክ እንደገና ተወልዶ ወደ ሕፃንነቱ ይመለሳል፤ ይህንን ሂደት ደግሞ ሳይሞት ለዘላለም ደጋግሞ ማከናወን ይችላል።
ተመራማሪዎች የዚህን ፍጡር የዲኤንኤ (DNA) ምስጢር ለመፍታት ሌሊትና ቀን እየሠሩ የሚገኙ ሲሆን፣ ግኝቱ ለሰው ልጅ የእርጅና መከላከያ እና የካንሰር ሕክምና ምርምር ትልቅ ተስፋን የፈነጠቀ በመሆኑ በማኅበራዊ ሚዲያና በሳይንሱ ዓለም ከፍተኛ መነጋገሪያ ሆኗል።
Seledadotio
Seledadotio
26 days ago
አስገዳጅ የክረምት ትምህርት ዓላማውን ያሳካል?
( መላኩ ብርሃኑ)
(ይህ ጽሁፍ ዘለግ ይላል፣ ማንበብ የማትችሉ እለፉት፣የሚገድዳችሁ ብቻ አንብቡት)
#ethiopia | በከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ ለሚማሩ የ11ኛና የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች በሙሉ በዚህ ክረምት ከሃምሌ 6 እስከ ነሃሴ 29 ቀን ለሁለት ወር የሚቆይ የግዴታ ትህምርት እንዲሰጥ በከተማው ትምህርት ቢሮ መመሪያ ወርዶ በየወረዳው ያሉ ትምህርት ቤቶችም እሱን ለመተግበር ተማሪዎችን መጥራት ጀምረዋል። ለአገልግሎቱ 1 ሺህ ብር ክፍያ መክፈልም ግዴታ ነው። እንደሰማሁት ከሆነ ፕሮግራሙ “የተማሪዎች እውቀት ማላቂያ ስትራተጂ” የሚባል ሲሆን ፣ ዓላማውም ተማሪዎችን ለመጪው የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ማዘጋጀት ነው።
ተማሪዎች በማጠናከሪያ ትምህርት መደገፋቸውና ለሚቀጥለው ክፍል ዝግጁ መደረጋቸው በድፍኑ ሲታይ መልካም ነው። ግን ደግሞ እዚህ ላይ ተማሪዎቹም ይሁኑ ወላጆች የሚያነሷቸው ጥያቄዎች ብዙ ናቸው።
እኔ ነገሩን በሁለት አቅጣጫ ማየት እፈልጋለሁ። ከተማሪዎችና ወላጅ ከ “ፍላጎትና ተገቢነት” እና ከ”ትምህርት ጥራት” አኳያ።
“ፍላጎት እና ፋይዳ ”
በፍላጎት ደረጃ የሁሉንም ወላጆች ወክዬ መናገር ባልችልም ቢያንስ በቅርቤ የማውቃቸው ደርዘን የሚያልፉ ወላጆች ሁሉ ( እኔን ጨምሮ) በዚህ ፕሮግራም አይስማሙም። ገሚሶቹ “ልጆቹ ለወራት ከከረሙበት አስጨናቂ እና የተደራረበ የትምህርት መርሃግብር አኳያ ቢያንስ በዚህ ክረምት እረፍት ማግኘት አለባቸው፣ በተጨማሪም ከመደበኛ ትምህርት ውጪ በሆኑ ሙያዎችና እውቀቶች (Extra-curricular activities) ራሳቸውን ‘ሪፍሬሽ’ በማድረግ አዕምሯቸውን ለሚቀጥለው ዘመን ትምህርት ማዘጋጀት ይገባቸዋል” የሚል ነው። ገሚሶቹ ወላጆች ደግሞ “ልጆቻችን በዚህ ክረምትና ብርድ በዝናብ እየተደበደቡ ትምህርት ቤት በመሄድና በመመለስ እንዲታክቱብን አንፈልግም፣ ክረምት የእረፍትና የመዝናናት ጊዜ ነው” ይላሉ።
More or less የሁለቱም ወገን አስተያየት ጭብጥ አንድ ነው። “ልጆች ረጅም ወራት ከተማሩ ፣ ለአጭር ጊዜ ደግሞ እረፍት ማግኘታቸው ግዴታ ነው። እንኳን ትኩረት የሚፈልገው ትምህርት ቀርቶ ያለእረፍት የሚካሄድ ማንኛውም እንቅስቃሴ ሁሉ ስልቹነት (Burnout) ያመጣል። ይህ ደግሞ የሚቀጥለውን ዘመን ትምህርት ብቃት ይጎዳዋል የሚል ነው። ይህ ሲጠቃለል ከጎንዮሽ ጉዳቱ አንጻር ሲመዘን የዚህን ፕሮግራም ፋይዳ (significance) አናሳ ያደርገዋል” የሚል ነው።
በሌላ በኩል ያነጋገርኳቸው መምህራንም ቢሆኑ እረፍት ማድረግ በሚፈልጉበት የክረምት ወራት የማስተማር ፍላጎት እንደሌላቸው ተረድቻለሁ። ማስተማር በተፈጥሮው ከባድ ስራ ነው። የአካልም የዐዕምሮም ዝለት ያመጣል። መምህራን ማረፍና ራሳቸውን ለመጪው ዘመን የማስተማር ስራ ማዘጋጀት ይገባቸዋል።ይህ ማለት ግን እግራቸውን ሰቅለው ሁለት ወር ይተኛሉ ማለት አይደለም።
በብዙ ጣልቃገብነት እየተካሄደ ባለ አስቸጋሪ የመማር ማስተማር ሂደት ውስጥ የመምህራን ስልቹነት ጎልቶ እየወጣ ነው። ይህን ስልቺነት ያመጣው ማስተማር ከተረጋጋ አካሄድ ይልቅ ሩጫ የበዛበት ስራ እየሆነ በመምጣቱ ነው። ሲጀምር የትምህርት ዓመቱና ለተማሪዎች የሚታደለው ቴክስት ቡክ አልተጣጣሙም። ቴክስት ቡኩ በሚገባ ተሸፍኖ ሳያልቅ ፈተና ይደርሳል። ቴክስት ቡኩ የያዘው ነገር ሁሉ በፈተና ውስጥ ስለሚካተት ፣ ፈተናው ተማሪዎች ያልተማሩትን ፖርሽን ጨምሮ ስለሚመጣ ብዙዎች ውጤታቸው እየተበላሸባቸው ነው።
ትምህርት ‘መጽሃፉን ለመጨረስ ሲባል’ በከፍተኛ ፍጥነት ስለሚካሄድ ተማሪዎች አንዱን ሳይይዙ ወደሌላው መዝለላቸው ልማድ እየሆነ መጥቷል። በዚህ ሳቢያ መምህራንም ለፍተው የተማሪን እርካታና የትምህርቱንም ውጤት ሳያገኙ እየቀሩ በስነልቡና ተዳክመዋል። ጥቂት እረፍት እና ቆም ብሎ ማሰብ ያስፈልጋቸዋል።
በክረምት ወር መምህራን ለቀጣዩ ዘመን ትምህርት እጅግ በጣም አስፈላጊ ስራ መስራት አለባቸው። ያለፈውን ዘመን የትምህርት ሂደትና ውጤት ይገመግማሉ። አዲስ ሌሰን ፕላን ያዘጋጃሉ። የደከሙትን የሚያበቁበት፣ ጎበዞቹን የሚያበረቱበት ስትራተጂ ይነድፋሉ። የመምህራን ስልጠናም በዚሁ ክረምት ነው የሚሰጠው።
ትምህርት ቤቶችም ቢሆኑ ግቢያቸውን ለመማር ማስተማር ዝግጁ ማድረግ አለባቸው። ህንጻ እድሳት፣ ቀለም ቅብ ፣ሜዳ ማስተካከል እና የተሰበሩ ወንበርና ጠረጴዛዎችን መጠገን የሚቀጥለው አመት ትምህርት ዝግጅት አካል ነው። ተማሪዎች በአዲሱ ዓመት ሲመጡ በትምህርት ቤታቸው ለየት ያለ ከባቢ ሲያገኙ የመማር ፍላጎታቸው ይጨምራል ተብሎ ይታመናል። በአጠቃላይ ክረምት ከተማሪም፣ ከመምህራንም፣ ከትምህርት ቤትም አንጻር የብዙ ነገር መስሪያ ጊዜ ነው።
“የትምህርት ጥራት”
ሁለተኛው በዚህ የክረምት ትምህርት ላይ ማንሳት የምፈልገው ጉዳይ የትምህርት ጥራት ጉዳይ ነው። የሃገራችን ትምህርት ትልቁ ካንሰር የትምህርት ጥራት አለመኖሩ ነው። ይህንን በሽታ ለማዳን በየዘርፉ የሚሞከሩ ስራዎችን አደንቃለሁ። ነገር ግን እንደክረምት ትምህርት ያሉ አንዳንድ እርምጃዎች የጋራ መግባባትን ይፈልጋሉ። ተማሪዎችና ወላጆች አምነውበት፣ መምህራንም ተቀብለውት ፣ ቢቻል ማትጊያ (Incentive) ታክሎበት ቢሆን የተሻለ ለውጥ ማምጣት ያስችላል።
ነገር ግን “ክረምት የማይማር ተማሪ በአዲሱ የትምህርት ዘመን መመዝገብ አይችልም፣ ሁሉንም ተማሪዎች በዚህ ፕሮግራም ያላካተተ ትምህርት ቤት ቅጣት ይጣልበታል” ብሎ ጉዳዩን ከጥቅሙ አኳያ ከመመዘንና ከማሳመን ፣ ሂደቱንምበጋራ መግባባት ላይ ከመመስረት ይልቅ የበላይ መመሪያን ለማስፈጸም (compliance) ብቻ ሲባል አስገዳጅ ክራይቴሪያ አድርጎ ማምጣት የትምህርት ጥራትን ያስጠብቃል ብዬ አላምንም።
ይህንን መመሪያ ግዴታ አድርጎ ከማውረድ በፊት ትምህርት ቤቶች፣ ወላጆችና መምህራንን ያካተተ የባለድርሻ አካላት ውይይት መካሄድ ነበረበት። እንዳለመታደል ሆኖ በየዘርፉ ባህል ያደረግነው አሰራር ከውይይት ይልቅ አስገዳጅ ነገር ላይ ያተኩራል። ከበላይ መመሪያ ወረደ ከተባለ ከሰማይ እንደመጣ ትዕዛዝ ጠፍንጎ ማስፈጸም የተለመደ ነው። ከመጣንበት መንገድ አልወጣንም። ከወታደራዊ ‘አድርግ አታድርግ’ ትዕዛዝ ለዘዘለ ሶስተኛ ሃሳብ ቦታ አንሰጥም። የውይይትና ባህል ስለሌለን እኛ ካልነው ተቃራኒ ድምጽ የመስማትን ትከሻ (Tolerance) አጥተናል። ይህም በማንኛውም ፕሮግራም ላይ የኔነት (ownership) ይዞ የሚሰራ ባለድርሻን ያሳጣናል።
ከዚህ ‘የማላቂያ’ ስትራተጂ ውስጥ በክረምት ትምህርት ፕሮግራም ላይ ወላጆችንና የየወረዳው የትምህርት ቢሮዎችን ያላስማማው አንዱ ጉዳይ ደግሞ ተማሪዎቹ እንዲማሩ የሚፈለገው በየትምህርት ቤቶቻቸው ውስጥ አለመሆኑ ነው። በተለይ የተሻለ ደረጃ ያላቸው የግል ትምህርት ቤት ተማሪዎች ወደሌላ የማያውቁት የመንግስት ሌላ ትምህርት ቤት ሄደው ተቀላቅለው እንዲማሩ መመሪያው ያስገድዳል። ይህ ደግሞ ወላጅ የትራንስፖርት፣ የአካባቢ አለመመቸትን እንዲያማርር፣ የተማሪዎች መድከም እና በሂደቱ ፍላጎት ማጣት እንዲከሰት መነሻ ሆኗል።
የመንግስት ትምህርት ቤት ተማሪዎች የተሻለ አቅም አላቸው ከሚባሉ የግል ትምህርት ቤት ተማሪዎች ጋር በጋራ መማራቸውና መወራረሳቸው የሚከፋ ሆኖ አይደለም። ግን የዚያ ‘ልምድ ልውውጥ’ ማስፈጸሚያ መንገድ የታሰበበትና የተጠና ፣ በአግባቡ ቁጥጥር የሚደረግበት አካሄድ የሚከተል ከመሆን ይልቅ ተማሪዎችን በዘፈቀደ መቀላቀልና ማስተማር ላይ ያተኮረ መሆኑ ላይ ነው ክፍተቱ። ይህም ‘ከኮቺንግ’ ይልቅ ወደትርጉም አልባ ውሎ መግባት አዘንብሏል። ቡድን ለይቶ ‘ቡሊ’ ወደመደራረግ አምርቷል። በተለይ ሴት ተማሪዎች በሂደቱ ላይ ያላቸው ፍላጎት እምብዛም ሆኖ ታይቷል። ይህም ከታሰበውን አላማ ስኬት ይልቅ የጎንዮሽ ጉዳቱ እንዲያመዝን አድርጎታል። ያለፈው አካሄድ ያመጣው ውጤት በትክክለኛ ዳታ ላይ ተመስርቶ የታየም አይመስለኝም።
“መፍትሄ”
ከላይ ከዘረዘርኳቸው ተማሪዎችና ወላጆችም ይሁን ከመምህራንና ትምህርት ቤቶች አንጻርም ስናየው ይህ በአካል ክፍል መገኘትን የሚጠይቅ የክረምት ትምህርት ፕሮግራም የሚፈለገውን ውጤት ያመጣል የሚል እምነት የለኝም። ሙሉ በሙሉ ይቅር የሚል አቋምም የለኝም። ቢሆን የተሻለ ነው የምለው የርቀት ድጋፍና ስልጠና (ኮቺንግ) ላይ ማትኮርን ነው።
ተማሪዎች ሳይጉላሉ፣ ወላጆች ሳይማረሩ፣ መምህራን ሳይሰላቹ፣ ክረምቱም ለሁሉም ተግባር በቂ ተመድቦለት እንዲካሄድ ተማሪዎችን ቤት እያሉ በሩቁ በዋና ወና ትምህርቶች ላይ ብቻ ኖት እየላኩ በቀን ለተወሰኑ ሰዓታት ብቻ እንዲያነቡና እንዲያጠኑ ማድረግ፣ የመርጃ መጽሃፍትንና የሚነበቡ ማቴሪያሎችን ሊንክ መላክ፣ ከዚያ ኖት ላይ ቴስት አውጥቶ መፈተን፣ የመጨረሻውን ፈተና ደግሞ በመስከረም ትምህርት ቤት ሲጀመር በአካል ማድረግ፣ ውጤቱንም በሚቀጥለው ትምህርት ዘመን ውጤት ላይ በመቶኛ መደመርና ትርጉም ወዳለው ለውጥ ማምጣት ይቻላል።
ለዚህ ስራ ለመምህራን ማትጊያ ክፍያ የሚሆን ከተማሪዎች በተመጣጣኝ ዋጋ ክፍያ መሰብሰብም ይቻላል። በዚህ ሂደት ማንም ‘ኮምፕሌይን’ ሳያደርግ የሚፈለገው ‘ማላቂያ’ ስትራተጂም ተፈጽሞ የትምህርት ጥራትም እንዲጠበቅ ማድረግ ይቻላል ብዬ አምናለሁ።
የጻፍኩት ሁሉ እንደአንድ የትምህርት ጥራት እንደሚያሳስበው ዜጋና ጠቃሚ ዜና ማፍራት እንደሚፈልግ አባት ያቀረብኩት የግል ሃሳቤ ነው፣ ማንኛውም የተለየም ይሁን ከዚህ ጋር የሚሄድ ሃሳብ ላለው ሰው መድረኩ ለውይይት ክፍት ነው። ሳንነጋገር በየቤታችን በማማረር እና በማልጎምጎም ለባሰ ውድቀት ከማዋጣት የዘለለ ተጨባጭ ለውጥ አናመጣም።
( መላኩ ብርሃኑ)
(ይህ ጽሁፍ ዘለግ ይላል፣ ማንበብ የማትችሉ እለፉት፣የሚገድዳችሁ ብቻ አንብቡት)
#ethiopia | በከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ ለሚማሩ የ11ኛና የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች በሙሉ በዚህ ክረምት ከሃምሌ 6 እስከ ነሃሴ 29 ቀን ለሁለት ወር የሚቆይ የግዴታ ትህምርት እንዲሰጥ በከተማው ትምህርት ቢሮ መመሪያ ወርዶ በየወረዳው ያሉ ትምህርት ቤቶችም እሱን ለመተግበር ተማሪዎችን መጥራት ጀምረዋል። ለአገልግሎቱ 1 ሺህ ብር ክፍያ መክፈልም ግዴታ ነው። እንደሰማሁት ከሆነ ፕሮግራሙ “የተማሪዎች እውቀት ማላቂያ ስትራተጂ” የሚባል ሲሆን ፣ ዓላማውም ተማሪዎችን ለመጪው የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ማዘጋጀት ነው።
ተማሪዎች በማጠናከሪያ ትምህርት መደገፋቸውና ለሚቀጥለው ክፍል ዝግጁ መደረጋቸው በድፍኑ ሲታይ መልካም ነው። ግን ደግሞ እዚህ ላይ ተማሪዎቹም ይሁኑ ወላጆች የሚያነሷቸው ጥያቄዎች ብዙ ናቸው።
እኔ ነገሩን በሁለት አቅጣጫ ማየት እፈልጋለሁ። ከተማሪዎችና ወላጅ ከ “ፍላጎትና ተገቢነት” እና ከ”ትምህርት ጥራት” አኳያ።
“ፍላጎት እና ፋይዳ ”
በፍላጎት ደረጃ የሁሉንም ወላጆች ወክዬ መናገር ባልችልም ቢያንስ በቅርቤ የማውቃቸው ደርዘን የሚያልፉ ወላጆች ሁሉ ( እኔን ጨምሮ) በዚህ ፕሮግራም አይስማሙም። ገሚሶቹ “ልጆቹ ለወራት ከከረሙበት አስጨናቂ እና የተደራረበ የትምህርት መርሃግብር አኳያ ቢያንስ በዚህ ክረምት እረፍት ማግኘት አለባቸው፣ በተጨማሪም ከመደበኛ ትምህርት ውጪ በሆኑ ሙያዎችና እውቀቶች (Extra-curricular activities) ራሳቸውን ‘ሪፍሬሽ’ በማድረግ አዕምሯቸውን ለሚቀጥለው ዘመን ትምህርት ማዘጋጀት ይገባቸዋል” የሚል ነው። ገሚሶቹ ወላጆች ደግሞ “ልጆቻችን በዚህ ክረምትና ብርድ በዝናብ እየተደበደቡ ትምህርት ቤት በመሄድና በመመለስ እንዲታክቱብን አንፈልግም፣ ክረምት የእረፍትና የመዝናናት ጊዜ ነው” ይላሉ።
More or less የሁለቱም ወገን አስተያየት ጭብጥ አንድ ነው። “ልጆች ረጅም ወራት ከተማሩ ፣ ለአጭር ጊዜ ደግሞ እረፍት ማግኘታቸው ግዴታ ነው። እንኳን ትኩረት የሚፈልገው ትምህርት ቀርቶ ያለእረፍት የሚካሄድ ማንኛውም እንቅስቃሴ ሁሉ ስልቹነት (Burnout) ያመጣል። ይህ ደግሞ የሚቀጥለውን ዘመን ትምህርት ብቃት ይጎዳዋል የሚል ነው። ይህ ሲጠቃለል ከጎንዮሽ ጉዳቱ አንጻር ሲመዘን የዚህን ፕሮግራም ፋይዳ (significance) አናሳ ያደርገዋል” የሚል ነው።
በሌላ በኩል ያነጋገርኳቸው መምህራንም ቢሆኑ እረፍት ማድረግ በሚፈልጉበት የክረምት ወራት የማስተማር ፍላጎት እንደሌላቸው ተረድቻለሁ። ማስተማር በተፈጥሮው ከባድ ስራ ነው። የአካልም የዐዕምሮም ዝለት ያመጣል። መምህራን ማረፍና ራሳቸውን ለመጪው ዘመን የማስተማር ስራ ማዘጋጀት ይገባቸዋል።ይህ ማለት ግን እግራቸውን ሰቅለው ሁለት ወር ይተኛሉ ማለት አይደለም።
በብዙ ጣልቃገብነት እየተካሄደ ባለ አስቸጋሪ የመማር ማስተማር ሂደት ውስጥ የመምህራን ስልቹነት ጎልቶ እየወጣ ነው። ይህን ስልቺነት ያመጣው ማስተማር ከተረጋጋ አካሄድ ይልቅ ሩጫ የበዛበት ስራ እየሆነ በመምጣቱ ነው። ሲጀምር የትምህርት ዓመቱና ለተማሪዎች የሚታደለው ቴክስት ቡክ አልተጣጣሙም። ቴክስት ቡኩ በሚገባ ተሸፍኖ ሳያልቅ ፈተና ይደርሳል። ቴክስት ቡኩ የያዘው ነገር ሁሉ በፈተና ውስጥ ስለሚካተት ፣ ፈተናው ተማሪዎች ያልተማሩትን ፖርሽን ጨምሮ ስለሚመጣ ብዙዎች ውጤታቸው እየተበላሸባቸው ነው።
ትምህርት ‘መጽሃፉን ለመጨረስ ሲባል’ በከፍተኛ ፍጥነት ስለሚካሄድ ተማሪዎች አንዱን ሳይይዙ ወደሌላው መዝለላቸው ልማድ እየሆነ መጥቷል። በዚህ ሳቢያ መምህራንም ለፍተው የተማሪን እርካታና የትምህርቱንም ውጤት ሳያገኙ እየቀሩ በስነልቡና ተዳክመዋል። ጥቂት እረፍት እና ቆም ብሎ ማሰብ ያስፈልጋቸዋል።
በክረምት ወር መምህራን ለቀጣዩ ዘመን ትምህርት እጅግ በጣም አስፈላጊ ስራ መስራት አለባቸው። ያለፈውን ዘመን የትምህርት ሂደትና ውጤት ይገመግማሉ። አዲስ ሌሰን ፕላን ያዘጋጃሉ። የደከሙትን የሚያበቁበት፣ ጎበዞቹን የሚያበረቱበት ስትራተጂ ይነድፋሉ። የመምህራን ስልጠናም በዚሁ ክረምት ነው የሚሰጠው።
ትምህርት ቤቶችም ቢሆኑ ግቢያቸውን ለመማር ማስተማር ዝግጁ ማድረግ አለባቸው። ህንጻ እድሳት፣ ቀለም ቅብ ፣ሜዳ ማስተካከል እና የተሰበሩ ወንበርና ጠረጴዛዎችን መጠገን የሚቀጥለው አመት ትምህርት ዝግጅት አካል ነው። ተማሪዎች በአዲሱ ዓመት ሲመጡ በትምህርት ቤታቸው ለየት ያለ ከባቢ ሲያገኙ የመማር ፍላጎታቸው ይጨምራል ተብሎ ይታመናል። በአጠቃላይ ክረምት ከተማሪም፣ ከመምህራንም፣ ከትምህርት ቤትም አንጻር የብዙ ነገር መስሪያ ጊዜ ነው።
“የትምህርት ጥራት”
ሁለተኛው በዚህ የክረምት ትምህርት ላይ ማንሳት የምፈልገው ጉዳይ የትምህርት ጥራት ጉዳይ ነው። የሃገራችን ትምህርት ትልቁ ካንሰር የትምህርት ጥራት አለመኖሩ ነው። ይህንን በሽታ ለማዳን በየዘርፉ የሚሞከሩ ስራዎችን አደንቃለሁ። ነገር ግን እንደክረምት ትምህርት ያሉ አንዳንድ እርምጃዎች የጋራ መግባባትን ይፈልጋሉ። ተማሪዎችና ወላጆች አምነውበት፣ መምህራንም ተቀብለውት ፣ ቢቻል ማትጊያ (Incentive) ታክሎበት ቢሆን የተሻለ ለውጥ ማምጣት ያስችላል።
ነገር ግን “ክረምት የማይማር ተማሪ በአዲሱ የትምህርት ዘመን መመዝገብ አይችልም፣ ሁሉንም ተማሪዎች በዚህ ፕሮግራም ያላካተተ ትምህርት ቤት ቅጣት ይጣልበታል” ብሎ ጉዳዩን ከጥቅሙ አኳያ ከመመዘንና ከማሳመን ፣ ሂደቱንምበጋራ መግባባት ላይ ከመመስረት ይልቅ የበላይ መመሪያን ለማስፈጸም (compliance) ብቻ ሲባል አስገዳጅ ክራይቴሪያ አድርጎ ማምጣት የትምህርት ጥራትን ያስጠብቃል ብዬ አላምንም።
ይህንን መመሪያ ግዴታ አድርጎ ከማውረድ በፊት ትምህርት ቤቶች፣ ወላጆችና መምህራንን ያካተተ የባለድርሻ አካላት ውይይት መካሄድ ነበረበት። እንዳለመታደል ሆኖ በየዘርፉ ባህል ያደረግነው አሰራር ከውይይት ይልቅ አስገዳጅ ነገር ላይ ያተኩራል። ከበላይ መመሪያ ወረደ ከተባለ ከሰማይ እንደመጣ ትዕዛዝ ጠፍንጎ ማስፈጸም የተለመደ ነው። ከመጣንበት መንገድ አልወጣንም። ከወታደራዊ ‘አድርግ አታድርግ’ ትዕዛዝ ለዘዘለ ሶስተኛ ሃሳብ ቦታ አንሰጥም። የውይይትና ባህል ስለሌለን እኛ ካልነው ተቃራኒ ድምጽ የመስማትን ትከሻ (Tolerance) አጥተናል። ይህም በማንኛውም ፕሮግራም ላይ የኔነት (ownership) ይዞ የሚሰራ ባለድርሻን ያሳጣናል።
ከዚህ ‘የማላቂያ’ ስትራተጂ ውስጥ በክረምት ትምህርት ፕሮግራም ላይ ወላጆችንና የየወረዳው የትምህርት ቢሮዎችን ያላስማማው አንዱ ጉዳይ ደግሞ ተማሪዎቹ እንዲማሩ የሚፈለገው በየትምህርት ቤቶቻቸው ውስጥ አለመሆኑ ነው። በተለይ የተሻለ ደረጃ ያላቸው የግል ትምህርት ቤት ተማሪዎች ወደሌላ የማያውቁት የመንግስት ሌላ ትምህርት ቤት ሄደው ተቀላቅለው እንዲማሩ መመሪያው ያስገድዳል። ይህ ደግሞ ወላጅ የትራንስፖርት፣ የአካባቢ አለመመቸትን እንዲያማርር፣ የተማሪዎች መድከም እና በሂደቱ ፍላጎት ማጣት እንዲከሰት መነሻ ሆኗል።
የመንግስት ትምህርት ቤት ተማሪዎች የተሻለ አቅም አላቸው ከሚባሉ የግል ትምህርት ቤት ተማሪዎች ጋር በጋራ መማራቸውና መወራረሳቸው የሚከፋ ሆኖ አይደለም። ግን የዚያ ‘ልምድ ልውውጥ’ ማስፈጸሚያ መንገድ የታሰበበትና የተጠና ፣ በአግባቡ ቁጥጥር የሚደረግበት አካሄድ የሚከተል ከመሆን ይልቅ ተማሪዎችን በዘፈቀደ መቀላቀልና ማስተማር ላይ ያተኮረ መሆኑ ላይ ነው ክፍተቱ። ይህም ‘ከኮቺንግ’ ይልቅ ወደትርጉም አልባ ውሎ መግባት አዘንብሏል። ቡድን ለይቶ ‘ቡሊ’ ወደመደራረግ አምርቷል። በተለይ ሴት ተማሪዎች በሂደቱ ላይ ያላቸው ፍላጎት እምብዛም ሆኖ ታይቷል። ይህም ከታሰበውን አላማ ስኬት ይልቅ የጎንዮሽ ጉዳቱ እንዲያመዝን አድርጎታል። ያለፈው አካሄድ ያመጣው ውጤት በትክክለኛ ዳታ ላይ ተመስርቶ የታየም አይመስለኝም።
“መፍትሄ”
ከላይ ከዘረዘርኳቸው ተማሪዎችና ወላጆችም ይሁን ከመምህራንና ትምህርት ቤቶች አንጻርም ስናየው ይህ በአካል ክፍል መገኘትን የሚጠይቅ የክረምት ትምህርት ፕሮግራም የሚፈለገውን ውጤት ያመጣል የሚል እምነት የለኝም። ሙሉ በሙሉ ይቅር የሚል አቋምም የለኝም። ቢሆን የተሻለ ነው የምለው የርቀት ድጋፍና ስልጠና (ኮቺንግ) ላይ ማትኮርን ነው።
ተማሪዎች ሳይጉላሉ፣ ወላጆች ሳይማረሩ፣ መምህራን ሳይሰላቹ፣ ክረምቱም ለሁሉም ተግባር በቂ ተመድቦለት እንዲካሄድ ተማሪዎችን ቤት እያሉ በሩቁ በዋና ወና ትምህርቶች ላይ ብቻ ኖት እየላኩ በቀን ለተወሰኑ ሰዓታት ብቻ እንዲያነቡና እንዲያጠኑ ማድረግ፣ የመርጃ መጽሃፍትንና የሚነበቡ ማቴሪያሎችን ሊንክ መላክ፣ ከዚያ ኖት ላይ ቴስት አውጥቶ መፈተን፣ የመጨረሻውን ፈተና ደግሞ በመስከረም ትምህርት ቤት ሲጀመር በአካል ማድረግ፣ ውጤቱንም በሚቀጥለው ትምህርት ዘመን ውጤት ላይ በመቶኛ መደመርና ትርጉም ወዳለው ለውጥ ማምጣት ይቻላል።
ለዚህ ስራ ለመምህራን ማትጊያ ክፍያ የሚሆን ከተማሪዎች በተመጣጣኝ ዋጋ ክፍያ መሰብሰብም ይቻላል። በዚህ ሂደት ማንም ‘ኮምፕሌይን’ ሳያደርግ የሚፈለገው ‘ማላቂያ’ ስትራተጂም ተፈጽሞ የትምህርት ጥራትም እንዲጠበቅ ማድረግ ይቻላል ብዬ አምናለሁ።
የጻፍኩት ሁሉ እንደአንድ የትምህርት ጥራት እንደሚያሳስበው ዜጋና ጠቃሚ ዜና ማፍራት እንደሚፈልግ አባት ያቀረብኩት የግል ሃሳቤ ነው፣ ማንኛውም የተለየም ይሁን ከዚህ ጋር የሚሄድ ሃሳብ ላለው ሰው መድረኩ ለውይይት ክፍት ነው። ሳንነጋገር በየቤታችን በማማረር እና በማልጎምጎም ለባሰ ውድቀት ከማዋጣት የዘለለ ተጨባጭ ለውጥ አናመጣም።
Comments