1 hr. ago
“መልእክተ ቅዱስ ፓትርያርክ"
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሓዱ አምላክ፣ አሜን !
በሀገር ውስጥና በመላው ዓለም የምትገኙ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን እምነት ተከታዮች በሙሉ!
የሰውን ወገን ለማዳን የልጁ ማደሪያ ትሆን ዘንድ ድንግል ማርያምን የመረጠ መፍቀሬ ሰብእ እግዚአብሔር ኣምላካችን እንኳን ለሁለት ሺሕ ዓሥራ ስምንት ዓመተ ምሕረት ጾመ ማርያም ኣደረሰን ኣደረሳችሁ!
“ወእመሰ ታፈቅሩኒ ዕቀቡ ትእዛዝየ፡- ከወደዳችሁኝስ ትእዛዜን ጠብቁ" (ዮሐ.14፥15)፤
ፍቅር የሕያዋን ኣካላት ረቂቅ መገናኛ ነው፣ ሕያዋን ኣካላት በውጫዊው ግዙፍ ኣካላቸው በተወሰኑ ጊዜያትና ቦታ ይገናኛሉ ፤ ስለ ጋራ ጉዳያቸውም በጋራ ይመክራሉ፤ ይበልጥም ይቀራረባሉ፡፡
ይሁንና የሕያዋን ኣካላት ግንኙነት በኣካል በጊዜና በቦታ ብቻ የተወሰነ ኣይደለም፣ በፍቅረ መንፈስ ተገናኝተውም ይግባባሉ፣ ከኣካላዊ ግንኙነት በላይ የበለጠም ይኸው ፍቅረ መንፈስ ነው፤ ከዚህ ኣንጻር እግዚአብሔርንም ማግኘት የምንችለው በዚሁ ፍቅረ መንፈስ ሆነን በእምነት ዓይን ነው!
ይህም በመሆኑ ሓዋርያው ቅዱስ ዮሓንስ በመልእክቱ “በፍቅር የሚኖር በእግዚአብሔርይኖራል፣ እግዚአብሔርም በእርሱ ይኖራል" በማለት ያስተምረናል፣ (1ዮሐ. 4፥16) ይህም ማለት ከሱ ጋር በፍቅር ስንገናኝ፤ እሱም በኛ፣ እኛም በእሱ የመኖሩ ኩነት ይፈጠራል ማለት ነው፡፡
የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ምእመናንና ምእመናት!
ጌታችን “አፍቅሮ ለእግዚአብሔር ኣምላክከ፤- አምላክህን እግዚአብሔርን ውደደው" በማለት በፍጹም ልባችን እንድንወደው፣ እንደዚሁም ራሳችንን በምንወድበት መጠን እርስ በእርሳችን እንድንዋደድ ማዘዙን እናውቃለን፤
የመውደዳችን መለኪያ ሚዛንና መገለጫ ምልክትም ትእዛዙን ማክበርና መጠበቅ እንደሆነ “ብትወዱኝስ ትእዛዜን ጠብቁ” በማለት ኣስተምሮናል ከዚህ ኣኳያ ጌታን መውደድ ማለት ትእዛዙን በመጠበቅ የሚገለጽ ግዙፍ ነገር እንጂ ምናባዊና የማይታይ ድብብቆሽ ነገር ኣይደለም ማለት ነው፣
ጌታችንን የመውደድ ነገር ትእዛዙን በመጠበቅ የሚገለጽ ከሆነ ትእዛዙ ምንድን ነው? የሚለውን ማየት ኣስፈላጊ ይሆናል፤ ትእዛዙን በጥቅል ስናይ እግዚአብሔርንና ባልንጀራን በመውደድ እንደሚጠቃለል ራሱ ጌታችን ኣስገንዝቦናል፣
በተለይም በባልንጀራችን ላይ የምንከተለው መውደድ ከላይ እንደተገለጸው “እንደራስህ ኣድርገህ ውደድ" ተብለ በግልጽ ተቀምጦኣል፤ የሰው ባልንጀራ እነማን ናቸው? በሕይወት ያሉት ናቸው? ወይስ የሞቱት? ወገን ዘመድ? ወይስ የሰው ወገን በሙሉ የሚለውንም ማወቅ ኣስፈላጊ ነው፡፡
ጌታችን ነገሩን በዚህ ደረጃ ለያይቶ ኣላስቀመጠም፣ ለምን? ቢባል ባልንጀራ ማለት የተወሰነን የማኅበረ ሰብ ወገን የሚያሳይ ሳይሆን መላውን የሰው ወገን የሚገልጽ በመሆኑ፤ እንደዚሁም የሞቱም ሆኑ ያለነው ሁላችን በእሱ ፊት ሕያዋንና እርስ በእርሳችን ባልንጀሮች በመሆናችን ነው፤
በመሆኑም መዋደዳችንም ሆነ መከባበራችን በሕይወተ ሥጋ ሳለን ብቻ ሳይሆን ከዚያም በኋላ እስከ በሌለው ዕድሜ በመሆኑ ጌታችን በጊዜ በቦታና በከፊል ለይቶ ኣላስቀመጠም፡፡
የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ምእመናንና ምእመናት !
ከነሐሴ ፩ ቀን ጀምሮ ለ፲፭ ቀናት የምንጾመው የጾመ ማርያም መነሻ ምክንያቱ የእግዚአብሔርትእዛዝና ፍቅር ነው፣
እግዚአብሔር ሰውን በኣጠቃላይ በተለይም ደግሞ እንደፈቃዱ የኖሩ ቅዱሳንን እንድናከብርኣዞናል ክቅዱሳን ፍጥረታት መካክል ደግሞ ቅድስት ድንግል ማርያም የመጀመሪያውን ደረጃ ትይዛለች፤
ይህም በመሆኑ ከፍጥረት ወገን ከሏ ክብር የሚደርስ ባለመኖሩ ከሁሉም ኣብልጠን እናክብራታለን፤
ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በዚህ ደረጃ የድንግል ማርያምን ክብር ስትገልጽ ክእግዚአብሔርና ለባስያነ እግዚአብሔር ክሆኑ ቀደምት ኣበው ተምራ ነው!
በአራተኛው መቶ ክፍለ ዘመን የነበረው ዕውቁ ቅዱስና ዓለም ዓቀፋዊው አባት ቅዱስ ኤፍሬም የድንግል ማርያምን ክብር! ቅድስና እና ልዕልና ሲናገር “ይእቲ ተዓቢ እምኪሩቤል፡ ወትፈደፍድ እምሱራፌል፣ እስመ ኮነት ታቦተ ለአሓዱ ዘእምቅድስት ሥላሴ- እሷ ከኪሩቤል ትበልጣለች! ከሱራፌልም ትልቃለች፣ ከቅድስት ሥላሴ ኣንዱ ለሆነው ታቦት ወይም ማደሪያ ሆናለችና" በማለት አስተምሮናል፡፡
በመሆኑም ለስሟ መታሰቢያ በሆነው በዚህ ጾም ድንግል ማርያምን በዚህ ደረጃ ስናክብርትእዛዙን እንጠብቃለን፤ ትእዛዙን በመጠበቃችን ደግሞ እሱን መውደዳችንን እናረጋግጣለን ! እኛ ድንግል ማርያምን እንድንወዳት "እናታችሁ'' ብሎ እንዳዘዘ፣ እሷም ልትወደን “ልጆችዅ ተብላ ታዛለችና ስለኛ ትጸልያለች፡፡
በጸሎቷም ከመከራ ትታደገናለች፤ በኣጠቃላይ በእግዚአብሔር' በቅዱሳንና በእኛ መካከል ያለው ግንኙነት በዚህ ትእዛዝና ፍቅር በትዕይንተ ዓለም ባለች ቤተ ክርስቲያን ዘንድ የተሳሰረ ነው፡፡
ስለሆነም በዚህ የጾመ ፍልሰታ ለማርያም ሱባዔ የተራቡትን በመመገብ፣ የታረዙትን በማልበስ፣ የተጣሎትን በማስታረቅ፤ የታመሙትንና የታስሩትን በመጠየቅ፤ ቅዱስ ቍርባንን በመቀበልና ለኃጢኣታችን የንሥሐ ሥርየትን በመለመን ሱባዔውን ልናሳልፍ ይገባል፡፡
በመጨረሻም
በሀገራችንም ሆነ በዓለም ዙሪያ ከባድ ስጋት የሆነው የፍጥረት ኣውዳሚ ጦርነትን በመለኮታዊ ጥበቡና ሥልጣኑ እንዲያስቆምልን በቅን ልቡና፤ በትሑት ሰብእና ሆነን እግዚአብሔርን በዚህ ሱባዔ እንድንጠይቀው ኣደራ ጭምር ኣባታዊ መልክታችንን በእግዚአብሔር ስም እናስተላልፋለን፤
የተባረከና የተቀደስ ጾም ያድርግልን፤
እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ሕዝቦችዋን ይባርክ!
ወስብሐት ለእግዚአብሔር፣ አሜን!
አባ ማትያስ ቀዳማዊ
ፓትርያርክ ርእስ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ
ሊቀ ጳጳስ ዘኣኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት
ነሐሴ 1 ቀን 2018 ዓ.ም
አዲስ አበባ፤ ኢትዮጵያ
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሓዱ አምላክ፣ አሜን !
በሀገር ውስጥና በመላው ዓለም የምትገኙ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን እምነት ተከታዮች በሙሉ!
የሰውን ወገን ለማዳን የልጁ ማደሪያ ትሆን ዘንድ ድንግል ማርያምን የመረጠ መፍቀሬ ሰብእ እግዚአብሔር ኣምላካችን እንኳን ለሁለት ሺሕ ዓሥራ ስምንት ዓመተ ምሕረት ጾመ ማርያም ኣደረሰን ኣደረሳችሁ!
“ወእመሰ ታፈቅሩኒ ዕቀቡ ትእዛዝየ፡- ከወደዳችሁኝስ ትእዛዜን ጠብቁ" (ዮሐ.14፥15)፤
ፍቅር የሕያዋን ኣካላት ረቂቅ መገናኛ ነው፣ ሕያዋን ኣካላት በውጫዊው ግዙፍ ኣካላቸው በተወሰኑ ጊዜያትና ቦታ ይገናኛሉ ፤ ስለ ጋራ ጉዳያቸውም በጋራ ይመክራሉ፤ ይበልጥም ይቀራረባሉ፡፡
ይሁንና የሕያዋን ኣካላት ግንኙነት በኣካል በጊዜና በቦታ ብቻ የተወሰነ ኣይደለም፣ በፍቅረ መንፈስ ተገናኝተውም ይግባባሉ፣ ከኣካላዊ ግንኙነት በላይ የበለጠም ይኸው ፍቅረ መንፈስ ነው፤ ከዚህ ኣንጻር እግዚአብሔርንም ማግኘት የምንችለው በዚሁ ፍቅረ መንፈስ ሆነን በእምነት ዓይን ነው!
ይህም በመሆኑ ሓዋርያው ቅዱስ ዮሓንስ በመልእክቱ “በፍቅር የሚኖር በእግዚአብሔርይኖራል፣ እግዚአብሔርም በእርሱ ይኖራል" በማለት ያስተምረናል፣ (1ዮሐ. 4፥16) ይህም ማለት ከሱ ጋር በፍቅር ስንገናኝ፤ እሱም በኛ፣ እኛም በእሱ የመኖሩ ኩነት ይፈጠራል ማለት ነው፡፡
የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ምእመናንና ምእመናት!
ጌታችን “አፍቅሮ ለእግዚአብሔር ኣምላክከ፤- አምላክህን እግዚአብሔርን ውደደው" በማለት በፍጹም ልባችን እንድንወደው፣ እንደዚሁም ራሳችንን በምንወድበት መጠን እርስ በእርሳችን እንድንዋደድ ማዘዙን እናውቃለን፤
የመውደዳችን መለኪያ ሚዛንና መገለጫ ምልክትም ትእዛዙን ማክበርና መጠበቅ እንደሆነ “ብትወዱኝስ ትእዛዜን ጠብቁ” በማለት ኣስተምሮናል ከዚህ ኣኳያ ጌታን መውደድ ማለት ትእዛዙን በመጠበቅ የሚገለጽ ግዙፍ ነገር እንጂ ምናባዊና የማይታይ ድብብቆሽ ነገር ኣይደለም ማለት ነው፣
ጌታችንን የመውደድ ነገር ትእዛዙን በመጠበቅ የሚገለጽ ከሆነ ትእዛዙ ምንድን ነው? የሚለውን ማየት ኣስፈላጊ ይሆናል፤ ትእዛዙን በጥቅል ስናይ እግዚአብሔርንና ባልንጀራን በመውደድ እንደሚጠቃለል ራሱ ጌታችን ኣስገንዝቦናል፣
በተለይም በባልንጀራችን ላይ የምንከተለው መውደድ ከላይ እንደተገለጸው “እንደራስህ ኣድርገህ ውደድ" ተብለ በግልጽ ተቀምጦኣል፤ የሰው ባልንጀራ እነማን ናቸው? በሕይወት ያሉት ናቸው? ወይስ የሞቱት? ወገን ዘመድ? ወይስ የሰው ወገን በሙሉ የሚለውንም ማወቅ ኣስፈላጊ ነው፡፡
ጌታችን ነገሩን በዚህ ደረጃ ለያይቶ ኣላስቀመጠም፣ ለምን? ቢባል ባልንጀራ ማለት የተወሰነን የማኅበረ ሰብ ወገን የሚያሳይ ሳይሆን መላውን የሰው ወገን የሚገልጽ በመሆኑ፤ እንደዚሁም የሞቱም ሆኑ ያለነው ሁላችን በእሱ ፊት ሕያዋንና እርስ በእርሳችን ባልንጀሮች በመሆናችን ነው፤
በመሆኑም መዋደዳችንም ሆነ መከባበራችን በሕይወተ ሥጋ ሳለን ብቻ ሳይሆን ከዚያም በኋላ እስከ በሌለው ዕድሜ በመሆኑ ጌታችን በጊዜ በቦታና በከፊል ለይቶ ኣላስቀመጠም፡፡
የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ምእመናንና ምእመናት !
ከነሐሴ ፩ ቀን ጀምሮ ለ፲፭ ቀናት የምንጾመው የጾመ ማርያም መነሻ ምክንያቱ የእግዚአብሔርትእዛዝና ፍቅር ነው፣
እግዚአብሔር ሰውን በኣጠቃላይ በተለይም ደግሞ እንደፈቃዱ የኖሩ ቅዱሳንን እንድናከብርኣዞናል ክቅዱሳን ፍጥረታት መካክል ደግሞ ቅድስት ድንግል ማርያም የመጀመሪያውን ደረጃ ትይዛለች፤
ይህም በመሆኑ ከፍጥረት ወገን ከሏ ክብር የሚደርስ ባለመኖሩ ከሁሉም ኣብልጠን እናክብራታለን፤
ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በዚህ ደረጃ የድንግል ማርያምን ክብር ስትገልጽ ክእግዚአብሔርና ለባስያነ እግዚአብሔር ክሆኑ ቀደምት ኣበው ተምራ ነው!
በአራተኛው መቶ ክፍለ ዘመን የነበረው ዕውቁ ቅዱስና ዓለም ዓቀፋዊው አባት ቅዱስ ኤፍሬም የድንግል ማርያምን ክብር! ቅድስና እና ልዕልና ሲናገር “ይእቲ ተዓቢ እምኪሩቤል፡ ወትፈደፍድ እምሱራፌል፣ እስመ ኮነት ታቦተ ለአሓዱ ዘእምቅድስት ሥላሴ- እሷ ከኪሩቤል ትበልጣለች! ከሱራፌልም ትልቃለች፣ ከቅድስት ሥላሴ ኣንዱ ለሆነው ታቦት ወይም ማደሪያ ሆናለችና" በማለት አስተምሮናል፡፡
በመሆኑም ለስሟ መታሰቢያ በሆነው በዚህ ጾም ድንግል ማርያምን በዚህ ደረጃ ስናክብርትእዛዙን እንጠብቃለን፤ ትእዛዙን በመጠበቃችን ደግሞ እሱን መውደዳችንን እናረጋግጣለን ! እኛ ድንግል ማርያምን እንድንወዳት "እናታችሁ'' ብሎ እንዳዘዘ፣ እሷም ልትወደን “ልጆችዅ ተብላ ታዛለችና ስለኛ ትጸልያለች፡፡
በጸሎቷም ከመከራ ትታደገናለች፤ በኣጠቃላይ በእግዚአብሔር' በቅዱሳንና በእኛ መካከል ያለው ግንኙነት በዚህ ትእዛዝና ፍቅር በትዕይንተ ዓለም ባለች ቤተ ክርስቲያን ዘንድ የተሳሰረ ነው፡፡
ስለሆነም በዚህ የጾመ ፍልሰታ ለማርያም ሱባዔ የተራቡትን በመመገብ፣ የታረዙትን በማልበስ፣ የተጣሎትን በማስታረቅ፤ የታመሙትንና የታስሩትን በመጠየቅ፤ ቅዱስ ቍርባንን በመቀበልና ለኃጢኣታችን የንሥሐ ሥርየትን በመለመን ሱባዔውን ልናሳልፍ ይገባል፡፡
በመጨረሻም
በሀገራችንም ሆነ በዓለም ዙሪያ ከባድ ስጋት የሆነው የፍጥረት ኣውዳሚ ጦርነትን በመለኮታዊ ጥበቡና ሥልጣኑ እንዲያስቆምልን በቅን ልቡና፤ በትሑት ሰብእና ሆነን እግዚአብሔርን በዚህ ሱባዔ እንድንጠይቀው ኣደራ ጭምር ኣባታዊ መልክታችንን በእግዚአብሔር ስም እናስተላልፋለን፤
የተባረከና የተቀደስ ጾም ያድርግልን፤
እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ሕዝቦችዋን ይባርክ!
ወስብሐት ለእግዚአብሔር፣ አሜን!
አባ ማትያስ ቀዳማዊ
ፓትርያርክ ርእስ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ
ሊቀ ጳጳስ ዘኣኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት
ነሐሴ 1 ቀን 2018 ዓ.ም
አዲስ አበባ፤ ኢትዮጵያ
2 hours ago
የደረጃ “ለ” ነጋዴዎች
👉መልእክት ያልደረሳችሁ ወይም
👉መልእክቱ ከሐምሌ 25 በኋላ የደረሳችሁ ያለቅጣት እስከ ነሐሴ 20 ቀን 2018 ዓ.ም መክፈል ስለምትችሉ በትዕግስት እንድትጠባበቁ ሲል የአ.አ ገቢዎች ቢሮ አሳስቧል።
ከሐምሌ 25 በፊት መልእክት የደረሳችሁ ግብር ከፋዮች ግን እስከ ሐምሌ 30 ቀን 2018 ዓ.ም በኦንላይን እንድትከፍሉ አሳስቧል።
የ2018 የግብር ዘመን የደረጃ “ለ” ግብር ከፋዮች አብዛኞቹ በኦንላይን የክፍያ ስርዓት ግብራቸውን መክፈላቸውና የተቀሩትም እየከፈሉ መሆኑ ተመላክቷል።
በከተማዋ በተለያዩ የንግድ ዘርፎች የተሰማሩ 456 ሺህ 433 የደረጃ “ለ” ግብር ከፋዮች እንደሚገኙና ከእነዚህ ግብር ከፋዮችም 9 ነጥብ 2 ቢሊየን ብር ለመሰብሰብ መታቀዱም ተገልጿል።
የደረጃ “ለ” ነጋዴዎች ግብር ከተቀጣሪዎች ያነሰ መሆኑና ይህም የሆነው የከተማ አስተዳደሩ አነስተኛ ነጋዴዎችን ለማበረታታትና ለማሳደግ ባለው ቁርጠኝነት ምክንያት እንደሆነ መግለጫው አመላክቷል።
እስከ ሐምሌ 25 መልእክት የደረሳችሁ ግብር ከፋዮች እስከ ሐምሌ 30 ቀን 2018 ዓ.ም በኦንላይን እንድትከፍሉ፣ መልእክት ያልደረሳችሁ ወይም ከሐምሌ 25 በኋላ የደረሳችሁ ደግሞ ያለቅጣት እስከ ነሐሴ 20 ቀን 2018 ዓ.ም መክፈል ስለምትችሉ በትዕግስት እንድትጠባበቁ ሲልም ቢሮው አሳስቧል።
ግብር በዛብኝ የሚል ቅሬታ ላለው ማንኛውም ግብር ከፋይ የቅሬታ አፈታት ስርዓት ተዘርግቶ ወደ ተግባር የተገባ መሆኑንም ጠቁሟል።
በስልክ የጽሁፍ መልዕክት የተላከው የደረጃ “ለ” ዓመታዊ ግብር፣ ግብር ከፋዮች በቅድመ ታክስ የከፈሉትን ገንዘብ ተቀናሽ አድርጎ የያዘ እንደሆነም ተገልጿል።(ምንጭ፣ የአ.አ ገቢዎች ቢሮ)
Seledadotio
Seledadotio
👉መልእክት ያልደረሳችሁ ወይም
👉መልእክቱ ከሐምሌ 25 በኋላ የደረሳችሁ ያለቅጣት እስከ ነሐሴ 20 ቀን 2018 ዓ.ም መክፈል ስለምትችሉ በትዕግስት እንድትጠባበቁ ሲል የአ.አ ገቢዎች ቢሮ አሳስቧል።
ከሐምሌ 25 በፊት መልእክት የደረሳችሁ ግብር ከፋዮች ግን እስከ ሐምሌ 30 ቀን 2018 ዓ.ም በኦንላይን እንድትከፍሉ አሳስቧል።
የ2018 የግብር ዘመን የደረጃ “ለ” ግብር ከፋዮች አብዛኞቹ በኦንላይን የክፍያ ስርዓት ግብራቸውን መክፈላቸውና የተቀሩትም እየከፈሉ መሆኑ ተመላክቷል።
በከተማዋ በተለያዩ የንግድ ዘርፎች የተሰማሩ 456 ሺህ 433 የደረጃ “ለ” ግብር ከፋዮች እንደሚገኙና ከእነዚህ ግብር ከፋዮችም 9 ነጥብ 2 ቢሊየን ብር ለመሰብሰብ መታቀዱም ተገልጿል።
የደረጃ “ለ” ነጋዴዎች ግብር ከተቀጣሪዎች ያነሰ መሆኑና ይህም የሆነው የከተማ አስተዳደሩ አነስተኛ ነጋዴዎችን ለማበረታታትና ለማሳደግ ባለው ቁርጠኝነት ምክንያት እንደሆነ መግለጫው አመላክቷል።
እስከ ሐምሌ 25 መልእክት የደረሳችሁ ግብር ከፋዮች እስከ ሐምሌ 30 ቀን 2018 ዓ.ም በኦንላይን እንድትከፍሉ፣ መልእክት ያልደረሳችሁ ወይም ከሐምሌ 25 በኋላ የደረሳችሁ ደግሞ ያለቅጣት እስከ ነሐሴ 20 ቀን 2018 ዓ.ም መክፈል ስለምትችሉ በትዕግስት እንድትጠባበቁ ሲልም ቢሮው አሳስቧል።
ግብር በዛብኝ የሚል ቅሬታ ላለው ማንኛውም ግብር ከፋይ የቅሬታ አፈታት ስርዓት ተዘርግቶ ወደ ተግባር የተገባ መሆኑንም ጠቁሟል።
በስልክ የጽሁፍ መልዕክት የተላከው የደረጃ “ለ” ዓመታዊ ግብር፣ ግብር ከፋዮች በቅድመ ታክስ የከፈሉትን ገንዘብ ተቀናሽ አድርጎ የያዘ እንደሆነም ተገልጿል።(ምንጭ፣ የአ.አ ገቢዎች ቢሮ)
Seledadotio
Seledadotio
5 hours ago
የቲቪ ፕሮግራም አቅራቢዋ እና የሶሻል ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪዋ ዳናዊት መክብብ ቀርቦባት በነበረው ክስ በነፃ ተሰናበተች።
ዳናዊት ከ ኤቢኤል ኮንሰልታንሲ ሀላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር፣ ቤተልሔም ታደሰ፣ ገሊላ በለጠ እና ቤል ተስፋዬ ከተባሉ ሌሎች ተከሳሾች ጋር የፍትሐብሔር ክስ የተመሰረተባት ከወራት በፊት እንደነበረ ይታወቃል።
ቁጥራቸው 13 የሆኑ ከሳሾች «እነ ዳናዊት ወደ ውጭ ሀገር እንልካችኋለን በማለት ከእያንዳንዳችን 437,000 ብር ከተቀበሉ በኋላ ሳይልኩን ቀርተዋል» በሚል ክስ ለፍርድ ቤት አቅርበውባቸው ነበር።
«የተወሰደብንን ገንዘብ እንዲመለስልን በተለያዩ ጊዜያት የቃል እና የጽሁፍ ማስጠንቀቂያ ብንሰጣቸውም እና ጉዳዩን በጋራ መግባባት ለመፍታት ጥረት ብናደርግም ተከሳሾች ብሩን ለመመለስም ሆነ ለማስመለስ እንቢተኛ ሆነዋል» ሲሉ ባስገቡት የክስ ዝርዝር ላይ አብራርተዋል።
አያይዘውም «እኛ ከሳሾች ወደዚህ ጉዳይ በሙሉ መተማመን የገባነው አምስተኛ ተከሳሽ የሆነችው ዳናዊት መክብብ ለድርጅቱ የሰራችውን ማስታወቂያ በማመን ነው» ሲሉ በክሳቸው ላይ ጠቅሰዋል።
ለወራት ክሱን ሲመለከት የቆየው የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ቦሌ ምድብ 4ኛ የፍትሐብሔር ችሎት ትናንት ሐምሌ 28 ቀን 2018 ዓ.ም በዋለው ችሎት አራቱን ተከሳሾች ጥፋተኛ በመሆናቸው በአንድነት እና በነጠላ ገንዘቡን ሊከፍሉ ይገባል ሲል ውሳኔ የሰጠ ሲሆን፣ አምስተኛ ተከሳሽ ዳናዊት መክብብ «ሥራን የሠራችው የንግድ ፈቃድ አይታ ነው፤ ስለዚህ ልትጠየቅ አይገባም» ከክሱ በነፃ ተሰናብታለች ሲል እንደወሰነ ሰምተናል።
ዘገባው የኢትዮጲካሊንክ ነው::
Seledadotio
Seledadotio
ዳናዊት ከ ኤቢኤል ኮንሰልታንሲ ሀላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር፣ ቤተልሔም ታደሰ፣ ገሊላ በለጠ እና ቤል ተስፋዬ ከተባሉ ሌሎች ተከሳሾች ጋር የፍትሐብሔር ክስ የተመሰረተባት ከወራት በፊት እንደነበረ ይታወቃል።
ቁጥራቸው 13 የሆኑ ከሳሾች «እነ ዳናዊት ወደ ውጭ ሀገር እንልካችኋለን በማለት ከእያንዳንዳችን 437,000 ብር ከተቀበሉ በኋላ ሳይልኩን ቀርተዋል» በሚል ክስ ለፍርድ ቤት አቅርበውባቸው ነበር።
«የተወሰደብንን ገንዘብ እንዲመለስልን በተለያዩ ጊዜያት የቃል እና የጽሁፍ ማስጠንቀቂያ ብንሰጣቸውም እና ጉዳዩን በጋራ መግባባት ለመፍታት ጥረት ብናደርግም ተከሳሾች ብሩን ለመመለስም ሆነ ለማስመለስ እንቢተኛ ሆነዋል» ሲሉ ባስገቡት የክስ ዝርዝር ላይ አብራርተዋል።
አያይዘውም «እኛ ከሳሾች ወደዚህ ጉዳይ በሙሉ መተማመን የገባነው አምስተኛ ተከሳሽ የሆነችው ዳናዊት መክብብ ለድርጅቱ የሰራችውን ማስታወቂያ በማመን ነው» ሲሉ በክሳቸው ላይ ጠቅሰዋል።
ለወራት ክሱን ሲመለከት የቆየው የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ቦሌ ምድብ 4ኛ የፍትሐብሔር ችሎት ትናንት ሐምሌ 28 ቀን 2018 ዓ.ም በዋለው ችሎት አራቱን ተከሳሾች ጥፋተኛ በመሆናቸው በአንድነት እና በነጠላ ገንዘቡን ሊከፍሉ ይገባል ሲል ውሳኔ የሰጠ ሲሆን፣ አምስተኛ ተከሳሽ ዳናዊት መክብብ «ሥራን የሠራችው የንግድ ፈቃድ አይታ ነው፤ ስለዚህ ልትጠየቅ አይገባም» ከክሱ በነፃ ተሰናብታለች ሲል እንደወሰነ ሰምተናል።
ዘገባው የኢትዮጲካሊንክ ነው::
Seledadotio
Seledadotio
13 hours ago
(ዘ-ሐበሻ ስፖርት) የቅድመ ውድድር ዘመን ዝግጅቱን እያደረገ የሚገኘው አርሰናል፣ በአየርላንዷ ዱብሊን ከተማ ከስፔኑ ሪያል ቤቲስ ጋር ባደረገው ጨዋታ ያልተጠበቀ ሽንፈት ማስተናገዱን ተከትሎ የተጫዋቾቹ ስሜት በእጅጉ መጎዳቱን አሰልጣኝ ሚኬል አርቴታ ገለጹ።
መድፈኞቹ ባልተለመደ ሁኔታ የመከላከያ ክፍላቸው ክፉኛ ተዳክሞ በታየበት የመጀመሪያው አጋማሽ ብቻ ሶስት ግቦችን ለማስተናገድ ተገደዋል። ምንም እንኳን ቤቲሶች የኳስ ቁጥጥሩን ለአርሰናል አሳልፈው ቢሰጡም፣ እጅግ አደገኛ በሆኑ ሙከራዎች እና ዒላማቸውን በጠበቁ ኳሶች የአርቴታን ልጆች ብልጫ ወስደውባቸዋል።
ከመጀመሪያው አጋማሽ መጥፎ አቋም በኋላ በመልበሻ ክፍል ውስጥ ስለነበረው ድባብ የተጠየቁት አርቴታ "በጣም ተበሳጭተዋል፣ ከባድ ጊዜ ነበር ያሳለፉት። በንዴት ጦፈዋል፤ ግን ይሄ ጥሩ ነው። እኛም የምንፈልገው ይሄንን ነው" ሲሉ ምላሽ ሰጥተዋል።
አርቴታ አክለውም "ዋናው ነገር ማሸነፍ ነበር፣ ግን አልቻልንም፤ ስለዚህ በውጤቱ ማዘናችን አይቀርም። ሆኖም መጥፎ ውጤት ማምጣት ለቀጣይ የተሻለ ስራ የድል ረሃብን ስለሚፈጥር አንዳንድ ጊዜ ጠቃሚ ነው" ብለዋል።
የዓለም ዋንጫ ተሳትፎን ተከትሎ ዴክላን ራይስ፣ ኤቤሬቺ ኤዜ፣ ኖኒ ማዱኤኬ እና ቡካዮ ሳካ አሁንም ስብስቡን አልተቀላቀሉም። የስፔን ብሔራዊ ቡድን ተጫዋቾቹ ሚኬል ሜሪኖ፣ ዴቪድ ራያ እና ማርቲን ዙቢሜንዲም እንዲሁ አልተመለሱም። አምበሉ ማርቲን ኦዴጋርድ ግን ከኖርዌይ ብሔራዊ ቡድን ተሳትፎው መልስ ግላዊ ልምምድ ጀምሯል።
ይሁን እንጂ አርሰናል እነዚህ ቁልፍ ተጫዋቾች ባይኖሩትም በቋሚ አሰላለፉ አራት ዓለም አቀፍ ተከላካዮችን፣ እንዲሁም ኢታን ኑዋኔሪ፣ ካይ ሃቨርትዝ፣ አዲሱ ፈራሚ ክሪስቶስ ዞሊስ እና ማክስ ዶውማንን በአማካይ ስፍራ፣ ቪክቶር ጊዮከረስን ደግሞ በአጥቂ መስመር አሰልፎ ነበር።
ባለፈው ሳምንት ጂሮናን 4-1 ባሸነፈበት አሰላለፍ ወደ ሜዳ የገባው አርሰናል፣ በጨዋታው መባቻ ጊዮከረስ ያገኘውን ግሩም አጋጣሚ የቤቲሱ ግብ ጠባቂ አልቫሮ ቫሌስ በእግሩ መልሶበታል። ሆኖም በ9ኛው ደቂቃ ላይ አርሰናሎች ጠንካራ ከሆኑበት የማዕዘን ምት ቤቲሶች ቀዳሚውን ግብ አግኝተዋል። ተቀያሪው ግብ ጠባቂ ኬፓ አሪዛባላጋ በፓብሎ ፎርናልስ የተመታውን ኳስ በአግባቡ ባለማንበቡ፣ ሮድሪጎ ሪኬልሜ ያለምንም ከልካይ ኳሷን መረብ ላይ አሳርፏል።
በአማካይ ስፍራ የተሰለፈው ወጣቱ ማይልስ ሉዊስ-ስኬሊ ከሌሎች የተሻለ እንቅስቃሴ ያሳየ ሲሆን፣ ሪካርዶ ካላፊዮሪ ወደ ፊት በሚሄድበት ጊዜ ቦታውን እየሸፈነ ድንቅ ስራ ሰርቷል። የግሪኩ ክንፍ ተጫዋች ዞሊስ የግብ ጠባቂውን ስህተት ተጠቅሞ አቻ የሚያደርግበትን ኳስ ቢያገኝም ኢላማውን ሳይጠብቅ ወደ ውጪ ወጥቶበታል።
ከ20 ዓመታት በኋላ ወደ ሻምፒዮንስ ሊግ የተመለሰው ሪያል ቤቲስ፣ በአርሰናል ስህተቶች ላይ በሚገባ ተጫውቷል። በ26ኛው ደቂቃ ኬፓ የሰራውን ደካማ የኳስ አወጣጥ ስህተት ተጠቅሞ ኔልሰን ዴኦሳ ከ25 ያርድ ርቀት ላይ አስደናቂ ግብ አስቆጥሯል። በ32ኛው ደቂቃ ዞሊስ ያሻገረውን ኳስ ፒዬሮ ሂንካፒ በጭንቅላቱ በመግጨት ለአርሰናል አንድ ግብ ቢመልስም፣ በ43ኛው ደቂቃ ላይ ካይ ሃቨርትዝ የሰራውን ስህተት ተጠቅሞ ፓብሎ ፎርናልስ የቤቲስን ሶስተኛ ግብ ከመረብ አዋህዷል።
በሁለተኛው አጋማሽ አርቴታ ጋብሪኤል ማርቲኔሊን እና ጋብሪኤል ማጋልሃስን ጨምሮ ሰባት ተጫዋቾችን ቀይረው አስገብተዋል። የ16 ዓመቱ ተከላካይ ማርሊ ሳልሞን እና የ19 ዓመቱ ሉዊ ኮፕሊም የመሰለፍ እድል ቢያገኙም፣ ኮፕሊ ገብቶ በሰባት ደቂቃ ውስጥ በደረሰበት የጉልበት ጉዳት ለመውጣት ተገዷል። በቅያሪዎች ብዛት የጨዋታው ምት የቀዘቀዘ ሲሆን፣ ጋብሪኤል ጄሱስ የተሻለ ሙከራ ቢያደርግም፣ አርቴታ በሜዳው ዳርቻ በብስጭት ሲንጎራደዱ ታይተዋል፤ መድፈኞቹም ያጡትን ክፍተት ማጥበብ ሳይችሉ ጨዋታው ተጠናቋል።
መድፈኞቹ ባልተለመደ ሁኔታ የመከላከያ ክፍላቸው ክፉኛ ተዳክሞ በታየበት የመጀመሪያው አጋማሽ ብቻ ሶስት ግቦችን ለማስተናገድ ተገደዋል። ምንም እንኳን ቤቲሶች የኳስ ቁጥጥሩን ለአርሰናል አሳልፈው ቢሰጡም፣ እጅግ አደገኛ በሆኑ ሙከራዎች እና ዒላማቸውን በጠበቁ ኳሶች የአርቴታን ልጆች ብልጫ ወስደውባቸዋል።
ከመጀመሪያው አጋማሽ መጥፎ አቋም በኋላ በመልበሻ ክፍል ውስጥ ስለነበረው ድባብ የተጠየቁት አርቴታ "በጣም ተበሳጭተዋል፣ ከባድ ጊዜ ነበር ያሳለፉት። በንዴት ጦፈዋል፤ ግን ይሄ ጥሩ ነው። እኛም የምንፈልገው ይሄንን ነው" ሲሉ ምላሽ ሰጥተዋል።
አርቴታ አክለውም "ዋናው ነገር ማሸነፍ ነበር፣ ግን አልቻልንም፤ ስለዚህ በውጤቱ ማዘናችን አይቀርም። ሆኖም መጥፎ ውጤት ማምጣት ለቀጣይ የተሻለ ስራ የድል ረሃብን ስለሚፈጥር አንዳንድ ጊዜ ጠቃሚ ነው" ብለዋል።
የዓለም ዋንጫ ተሳትፎን ተከትሎ ዴክላን ራይስ፣ ኤቤሬቺ ኤዜ፣ ኖኒ ማዱኤኬ እና ቡካዮ ሳካ አሁንም ስብስቡን አልተቀላቀሉም። የስፔን ብሔራዊ ቡድን ተጫዋቾቹ ሚኬል ሜሪኖ፣ ዴቪድ ራያ እና ማርቲን ዙቢሜንዲም እንዲሁ አልተመለሱም። አምበሉ ማርቲን ኦዴጋርድ ግን ከኖርዌይ ብሔራዊ ቡድን ተሳትፎው መልስ ግላዊ ልምምድ ጀምሯል።
ይሁን እንጂ አርሰናል እነዚህ ቁልፍ ተጫዋቾች ባይኖሩትም በቋሚ አሰላለፉ አራት ዓለም አቀፍ ተከላካዮችን፣ እንዲሁም ኢታን ኑዋኔሪ፣ ካይ ሃቨርትዝ፣ አዲሱ ፈራሚ ክሪስቶስ ዞሊስ እና ማክስ ዶውማንን በአማካይ ስፍራ፣ ቪክቶር ጊዮከረስን ደግሞ በአጥቂ መስመር አሰልፎ ነበር።
ባለፈው ሳምንት ጂሮናን 4-1 ባሸነፈበት አሰላለፍ ወደ ሜዳ የገባው አርሰናል፣ በጨዋታው መባቻ ጊዮከረስ ያገኘውን ግሩም አጋጣሚ የቤቲሱ ግብ ጠባቂ አልቫሮ ቫሌስ በእግሩ መልሶበታል። ሆኖም በ9ኛው ደቂቃ ላይ አርሰናሎች ጠንካራ ከሆኑበት የማዕዘን ምት ቤቲሶች ቀዳሚውን ግብ አግኝተዋል። ተቀያሪው ግብ ጠባቂ ኬፓ አሪዛባላጋ በፓብሎ ፎርናልስ የተመታውን ኳስ በአግባቡ ባለማንበቡ፣ ሮድሪጎ ሪኬልሜ ያለምንም ከልካይ ኳሷን መረብ ላይ አሳርፏል።
በአማካይ ስፍራ የተሰለፈው ወጣቱ ማይልስ ሉዊስ-ስኬሊ ከሌሎች የተሻለ እንቅስቃሴ ያሳየ ሲሆን፣ ሪካርዶ ካላፊዮሪ ወደ ፊት በሚሄድበት ጊዜ ቦታውን እየሸፈነ ድንቅ ስራ ሰርቷል። የግሪኩ ክንፍ ተጫዋች ዞሊስ የግብ ጠባቂውን ስህተት ተጠቅሞ አቻ የሚያደርግበትን ኳስ ቢያገኝም ኢላማውን ሳይጠብቅ ወደ ውጪ ወጥቶበታል።
ከ20 ዓመታት በኋላ ወደ ሻምፒዮንስ ሊግ የተመለሰው ሪያል ቤቲስ፣ በአርሰናል ስህተቶች ላይ በሚገባ ተጫውቷል። በ26ኛው ደቂቃ ኬፓ የሰራውን ደካማ የኳስ አወጣጥ ስህተት ተጠቅሞ ኔልሰን ዴኦሳ ከ25 ያርድ ርቀት ላይ አስደናቂ ግብ አስቆጥሯል። በ32ኛው ደቂቃ ዞሊስ ያሻገረውን ኳስ ፒዬሮ ሂንካፒ በጭንቅላቱ በመግጨት ለአርሰናል አንድ ግብ ቢመልስም፣ በ43ኛው ደቂቃ ላይ ካይ ሃቨርትዝ የሰራውን ስህተት ተጠቅሞ ፓብሎ ፎርናልስ የቤቲስን ሶስተኛ ግብ ከመረብ አዋህዷል።
በሁለተኛው አጋማሽ አርቴታ ጋብሪኤል ማርቲኔሊን እና ጋብሪኤል ማጋልሃስን ጨምሮ ሰባት ተጫዋቾችን ቀይረው አስገብተዋል። የ16 ዓመቱ ተከላካይ ማርሊ ሳልሞን እና የ19 ዓመቱ ሉዊ ኮፕሊም የመሰለፍ እድል ቢያገኙም፣ ኮፕሊ ገብቶ በሰባት ደቂቃ ውስጥ በደረሰበት የጉልበት ጉዳት ለመውጣት ተገዷል። በቅያሪዎች ብዛት የጨዋታው ምት የቀዘቀዘ ሲሆን፣ ጋብሪኤል ጄሱስ የተሻለ ሙከራ ቢያደርግም፣ አርቴታ በሜዳው ዳርቻ በብስጭት ሲንጎራደዱ ታይተዋል፤ መድፈኞቹም ያጡትን ክፍተት ማጥበብ ሳይችሉ ጨዋታው ተጠናቋል።
Sponsored by
Surafel
14 hours ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) ኢትዮጵያ ለግማሽ ምዕተ ዓመት ገደማ የውጭ ባንኮች በሀገሪቱ የፋይናንስ ዘርፍ ውስጥ እንዳይገቡ የጣለችውን እገዳ አንስታለች። በሰኔ 2025 በወጣው ታሪካዊ መመሪያ መሰረት፣ ዓለም አቀፍ አበዳሪዎች ቅርንጫፎችን መክፈት፣ የራሳቸውን ተቋም ማቋቋም እና በልዩ ሁኔታዎች የሀገር ውስጥ ባንኮችን ሙሉ በሙሉ መግዛት የሚችሉበት ዕድል ተፈጥሯል። ይሁን እንጂ ውሳኔው ከተላለፈ ከአንድ ዓመት በኋላ፣ የአፍሪካ ግዙፍ ባንኮች ከፍተኛ ፍላጎት ቢያሳዩም እስካሁን በተግባር ወደ ገበያው የገባ የውጭ ባንክ የለም።
ይህ ታሪካዊ እርምጃ የጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ የሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ አጀንዳ አካል ነው። የባንክ ስራ አዋጅ ቁጥር 1360/2024 በታህሳስ 2024 በፓርላማ ፀድቆ በመጋቢት 2025 በነጋሪት ጋዜጣ ታትሟል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክም በሰኔ 2025 የውጭ ባንኮችን የፍቃድ አሰጣጥ የሚገዛውን መመሪያ ይፋ አድርጓል።
መመሪያው የውጭ ባንኮች ወደ ገበያው የሚገቡባቸውን አምስት መንገዶች ቢያስቀምጥም፣ ጥብቅ የባለቤትነት ገደቦችን አስቀምጧል። በአንድ ባንክ ውስጥ የውጭ ዜጎች አጠቃላይ የባለቤትነት ድርሻ ከ49 በመቶ መብለጥ አይችልም። አንድ ስትራቴጂካዊ የውጭ ባለሀብት እስከ 40 በመቶ ብቻ መያዝ ሲችል፣ የውጭ ኩባንያዎች እስከ 10 በመቶ፣ እንዲሁም ግለሰቦች እስከ 7 በመቶ ድርሻ ብቻ ሊኖራቸው ይችላል። በተጨማሪም ማንኛውም የውጭ ባንክ ቅርንጫፍ ወይም ተቋም ሲያቋቁም ቢያንስ 5 ቢሊዮን ብር (በወቅቱ የምንዛሬ ተመን 32 ሚሊዮን ዶላር) የተከፈለ ካፒታል በውጭ ምንዛሬ እና በጥሬ ገንዘብ (በተዘዋዋሪ ክፍያ ሳይሆን) ማምጣት ይጠበቅበታል።
እስካሁን ቢያንስ ሰባት ትልልቅ የአፍሪካ ባንኮች ወደ ኢትዮጵያ ገበያ የመግባት ፍላጎት አሳይተዋል። በጠቅላላ ሀብቱ በአፍሪካ ትልቁ ባንክ የሆነው ስታንዳርድ ባንክ ግሩፕ፣ በህዳር 2025 በአዲሱ ማዕቀፍ መሰረት የውክልና ቢሮውን ፈቃድ ያደሰ የመጀመሪያው የውጭ ተቋም ሲሆን፣ አሁን ላይ ከባዶ የራሱን ባንክ ስለማቋቋም እያሰበ ይገኛል። የምስራቅ አፍሪካው ግዙፍ አበዳሪ ኬሲቢ ግሩፕ በ2026 መገባደጃ ላይ ሙሉ በሙሉ ወደ ገበያው ለመግባት እያለመ ሲሆን፣ ለዚህም ከሀገር ውስጥ አጋር ጋር አብሮ ለመስራት እያፈላለገ ይገኛል።
በተመሳሳይ የኬንያው ከፍተኛ ትርፋማ ባንክ ኢኩዊቲ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈፃሚ ከመንግስት የኢንቨስትመንት ኮሚሽን ጋር በሴፕቴምበር 2025 ቀጥተኛ ውይይት አድርገዋል። ከነዚህም በተጨማሪ እንደ የደቡብ አፍሪካው አብሳ፣ የጅቡቲው ቢሲአይኤምአር፣ እንዲሁም የናይጄሪያዎቹ ዜኒዝ እና ፈርስት ባንክ ገበያውን እና አማራጮችን በማጥናት ላይ እንደሚገኙ ታውቋል።
በባንኮቹ በኩል ከፍተኛ ፍላጎት ቢኖርም እስካሁን በተግባር ወደ ስራ ያልገቡባቸው ዋና ዋና ምክንያቶች አሉ። የመጀመሪያው ጉዳይ የ49 በመቶው የባለቤትነት ድርሻ ገደብ ነው። አብዛኛዎቹ የውጭ ባንኮች አዲስ ገበያ ሲገቡ የአብላጫ ድርሻ መያዝ ይፈልጋሉ። ነገር ግን ይህ ገደብ በስትራቴጂ፣ በአስተዳደር እና በካፒታል ድልድል ላይ ያላቸውን ውሳኔ ሰጪነት ስለሚገድበው አንዳንዶቹን የባለቤትነት ጣራው እስኪሻሻል እንዲያመነቱ አድርጓቸዋል።
ቀጣዩ ምክንያት የውጭ ምንዛሬ እና የዕዳ ስጋት ነው። መንግስት የውጭ ምንዛሬ ተመኑን በገበያ እንዲወሰን ማድረጉ በጎ እርምጃ ቢሆንም፣ ኢትዮጵያ በታህሳስ 2023 የ1 ቢሊዮን ዶላር የዩሮቦንድ እዳዋን መክፈል አለመቻሏ እና ያላት አነስተኛ የውጭ ምንዛሬ ክምችት የውጭ ባንኮችን አሳስቧል። እነዚህ ባንኮች ትርፋቸውን በውጭ ምንዛሬ ወደ ሀገራቸው ይዘው መውጣት ስለመቻላቸው እርግጠኛ መሆን ይፈልጋሉ።
በመጨረሻም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የውጭ ባንኮችን በፍጥነት ከማስገባት ይልቅ በመጀመሪያ የሀገር ውስጥ ባንኮችን አቅም ለማጠናከር ትኩረት መስጠቱ ለዘገየው ሒደት ሌላኛው ምክንያት ነው። የባንኮች ዝቅተኛ የተከፈለ ካፒታል ወደ 5 ቢሊዮን ብር ከፍ እንዲል በማድረግ ባንኮች አቅማቸውን እንዲያጎለብቱ ወይም እንዲዋሃዱ ግፊት እያደረገ ነው። ከዚህ ጋር ተያይዞ በቅርቡ ስራ የጀመረው የኢትዮጵያ ሰነደ ሙአለነዋይ ገበያ ለሀገር ውስጥ ባንኮች ተጨማሪ ካፒታል የማሰባሰቢያ መድረክ ሆኖላቸዋል።
እስካሁን የውጭ ባንክ ፈቃድ አለመሰጠቱ የሪፎርሙን ውድቀት አያሳይም፤ ይልቁንም የሽግግሩ ሂደት ከመጀመሪያው የዜና ጩኸት ይልቅ በተረጋጋ እና በጥንቃቄ እየሄደ መሆኑን ያመላክታል። ትልቁ ጥያቄ ያለው የኢትዮጵያ መንግስት በቀጣይ በባለቤትነት ገደቦች፣ በካፒታል እና በውጭ ምንዛሬ አቅርቦት ዙሪያ ያሉትን ጥብቅ ደንቦች ምን ያህል ያላግባቸዋል በሚለው ላይ የተመሰረተ ነው።
ይህ ታሪካዊ እርምጃ የጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ የሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ አጀንዳ አካል ነው። የባንክ ስራ አዋጅ ቁጥር 1360/2024 በታህሳስ 2024 በፓርላማ ፀድቆ በመጋቢት 2025 በነጋሪት ጋዜጣ ታትሟል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክም በሰኔ 2025 የውጭ ባንኮችን የፍቃድ አሰጣጥ የሚገዛውን መመሪያ ይፋ አድርጓል።
መመሪያው የውጭ ባንኮች ወደ ገበያው የሚገቡባቸውን አምስት መንገዶች ቢያስቀምጥም፣ ጥብቅ የባለቤትነት ገደቦችን አስቀምጧል። በአንድ ባንክ ውስጥ የውጭ ዜጎች አጠቃላይ የባለቤትነት ድርሻ ከ49 በመቶ መብለጥ አይችልም። አንድ ስትራቴጂካዊ የውጭ ባለሀብት እስከ 40 በመቶ ብቻ መያዝ ሲችል፣ የውጭ ኩባንያዎች እስከ 10 በመቶ፣ እንዲሁም ግለሰቦች እስከ 7 በመቶ ድርሻ ብቻ ሊኖራቸው ይችላል። በተጨማሪም ማንኛውም የውጭ ባንክ ቅርንጫፍ ወይም ተቋም ሲያቋቁም ቢያንስ 5 ቢሊዮን ብር (በወቅቱ የምንዛሬ ተመን 32 ሚሊዮን ዶላር) የተከፈለ ካፒታል በውጭ ምንዛሬ እና በጥሬ ገንዘብ (በተዘዋዋሪ ክፍያ ሳይሆን) ማምጣት ይጠበቅበታል።
እስካሁን ቢያንስ ሰባት ትልልቅ የአፍሪካ ባንኮች ወደ ኢትዮጵያ ገበያ የመግባት ፍላጎት አሳይተዋል። በጠቅላላ ሀብቱ በአፍሪካ ትልቁ ባንክ የሆነው ስታንዳርድ ባንክ ግሩፕ፣ በህዳር 2025 በአዲሱ ማዕቀፍ መሰረት የውክልና ቢሮውን ፈቃድ ያደሰ የመጀመሪያው የውጭ ተቋም ሲሆን፣ አሁን ላይ ከባዶ የራሱን ባንክ ስለማቋቋም እያሰበ ይገኛል። የምስራቅ አፍሪካው ግዙፍ አበዳሪ ኬሲቢ ግሩፕ በ2026 መገባደጃ ላይ ሙሉ በሙሉ ወደ ገበያው ለመግባት እያለመ ሲሆን፣ ለዚህም ከሀገር ውስጥ አጋር ጋር አብሮ ለመስራት እያፈላለገ ይገኛል።
በተመሳሳይ የኬንያው ከፍተኛ ትርፋማ ባንክ ኢኩዊቲ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈፃሚ ከመንግስት የኢንቨስትመንት ኮሚሽን ጋር በሴፕቴምበር 2025 ቀጥተኛ ውይይት አድርገዋል። ከነዚህም በተጨማሪ እንደ የደቡብ አፍሪካው አብሳ፣ የጅቡቲው ቢሲአይኤምአር፣ እንዲሁም የናይጄሪያዎቹ ዜኒዝ እና ፈርስት ባንክ ገበያውን እና አማራጮችን በማጥናት ላይ እንደሚገኙ ታውቋል።
በባንኮቹ በኩል ከፍተኛ ፍላጎት ቢኖርም እስካሁን በተግባር ወደ ስራ ያልገቡባቸው ዋና ዋና ምክንያቶች አሉ። የመጀመሪያው ጉዳይ የ49 በመቶው የባለቤትነት ድርሻ ገደብ ነው። አብዛኛዎቹ የውጭ ባንኮች አዲስ ገበያ ሲገቡ የአብላጫ ድርሻ መያዝ ይፈልጋሉ። ነገር ግን ይህ ገደብ በስትራቴጂ፣ በአስተዳደር እና በካፒታል ድልድል ላይ ያላቸውን ውሳኔ ሰጪነት ስለሚገድበው አንዳንዶቹን የባለቤትነት ጣራው እስኪሻሻል እንዲያመነቱ አድርጓቸዋል።
ቀጣዩ ምክንያት የውጭ ምንዛሬ እና የዕዳ ስጋት ነው። መንግስት የውጭ ምንዛሬ ተመኑን በገበያ እንዲወሰን ማድረጉ በጎ እርምጃ ቢሆንም፣ ኢትዮጵያ በታህሳስ 2023 የ1 ቢሊዮን ዶላር የዩሮቦንድ እዳዋን መክፈል አለመቻሏ እና ያላት አነስተኛ የውጭ ምንዛሬ ክምችት የውጭ ባንኮችን አሳስቧል። እነዚህ ባንኮች ትርፋቸውን በውጭ ምንዛሬ ወደ ሀገራቸው ይዘው መውጣት ስለመቻላቸው እርግጠኛ መሆን ይፈልጋሉ።
በመጨረሻም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የውጭ ባንኮችን በፍጥነት ከማስገባት ይልቅ በመጀመሪያ የሀገር ውስጥ ባንኮችን አቅም ለማጠናከር ትኩረት መስጠቱ ለዘገየው ሒደት ሌላኛው ምክንያት ነው። የባንኮች ዝቅተኛ የተከፈለ ካፒታል ወደ 5 ቢሊዮን ብር ከፍ እንዲል በማድረግ ባንኮች አቅማቸውን እንዲያጎለብቱ ወይም እንዲዋሃዱ ግፊት እያደረገ ነው። ከዚህ ጋር ተያይዞ በቅርቡ ስራ የጀመረው የኢትዮጵያ ሰነደ ሙአለነዋይ ገበያ ለሀገር ውስጥ ባንኮች ተጨማሪ ካፒታል የማሰባሰቢያ መድረክ ሆኖላቸዋል።
እስካሁን የውጭ ባንክ ፈቃድ አለመሰጠቱ የሪፎርሙን ውድቀት አያሳይም፤ ይልቁንም የሽግግሩ ሂደት ከመጀመሪያው የዜና ጩኸት ይልቅ በተረጋጋ እና በጥንቃቄ እየሄደ መሆኑን ያመላክታል። ትልቁ ጥያቄ ያለው የኢትዮጵያ መንግስት በቀጣይ በባለቤትነት ገደቦች፣ በካፒታል እና በውጭ ምንዛሬ አቅርቦት ዙሪያ ያሉትን ጥብቅ ደንቦች ምን ያህል ያላግባቸዋል በሚለው ላይ የተመሰረተ ነው።
15 hours ago
የCPJ የ2026 ዓለም አቀፍ የፕሬስ ነፃነት ሽልማት አሸናፊዎች ተገለጹ
#ethiopia | የጋዜጠኞችን ጥበቃ ኮሚቴ (CPJ) ለ36ኛ ጊዜ የሚያዘጋጀውን ዓመታዊ International Press Freedom Awards (IPFA) የ2026 ተሸላሚ ጋዜጠኞችን ይፋ አድርጓል።
የሽልማት ሥነ ሥርዓቱ ኅዳር 19 ቀን 2026 በኒውዮርክ ከተማ የሚካሄድ ሲሆን፣ ከተለያዩ አገራት የተውጣጡ ጋዜጠኞች በድፍረታቸውና በሙያዊ ተግባራቸው ይሸለማሉ።
በዚህ ዓመት ከተሸለሙት መካከል ከሊባኖስ፣ ከኤርትራ፣ ከሀንጋሪ፣ ከኮሎምቢያ እና ከሚያንማር የመጡ ጋዜጠኞች ይገኛሉ።
ክርስቲና አሲ – ሊባኖስ
የAFP ፎቶ ጋዜጠኛ ክርስቲና አሲ በጥቅምት 2023 በእስራኤል–ሊባኖስ ድንበር ዘገባ ስትሰራ በደረሰባት ጥቃት ቀኝ እግሯን አጥታለች፤ የሮይተርስ ጋዜጠኛ ኢሳም አብዳላህም በዚያው ጥቃት ተገድሏል።
CPJ እንደሚለው፣ በዚህ ጉዳይ እስካሁን ተጠያቂ የሆነ አካል የለም። አሲ ከዚያ በኋላ ለጋዜጠኞች ደኅንነትና ለፍትሕ ድምፅ ሆና እየሠራች ነው።
"ኤርትራ 16"
CPJ በዚህ ዓመት ለ25 ዓመታት ያለ ፍርድ ታስረው የቆዩትን "ኤርትራ 16" የተባሉ 16 ጋዜጠኞች በጋራ ሸልሟል።
እነዚህ ጋዜጠኞች በ2001 የግል ሚዲያዎች ከተዘጉ በኋላ ታስረው ሲሆን፣ እስካሁን ክስ አልቀረበባቸውም፣ ፍርድ ቤትም አልቀረቡም። የጤናቸውና የሕይወታቸው ሁኔታ እንኳን በግልፅ አይታወቅም።
ሳቦልች ፓንዪ – ሀንጋሪ
የምርመራ ጋዜጠኛው ሳቦልች ፓንዪ የሩሲያ ተፅዕኖ፣ ሙስናና የፖለቲካ ሥልጣን ላይ በሠራቸው ዘገባዎች የሚታወቅ ሲሆን፣ በ2026 የሀንጋሪ ምርጫ ዋዜማ ከባድ ጫናና የስለላ ክስ ተጋፍጦበታል።
ኤስቴፋኒ ሮድሪጌዝ – ኮሎምቢያ
በአሜሪካ የስፓኒሽ ቋንቋ ሚዲያ Nashville Noticias ዘጋቢ የሆነችው ኤስቴፋኒ ሮድሪጌዝ በ2026 በICE ተይዛ ታስራ ነበር።
CPJ ጉዳዩ በስደተኞች ጉዳይ ላይ በምታደርገው ዘገባ ምክንያት በጋዜጠኞች ላይ የሚደረግ ጫናን የሚያሳይ ነው ብሏል።
ሳይ ዛው ታይክ – ሚያንማር
የMyanmar Now ፎቶ ጋዜጠኛ ሳይ ዛው ታይክ በ2023 የCyclone Mocha ጉዳትን ሲዘግብ ተይዞ 20 ዓመት ከባድ እስራት ተፈርዶበታል።
CPJ እንደሚለው ሚያንማር በዓለም ላይ ጋዜጠኞችን በእስር ከሚያቆዩ አገራት መካከል ሁለተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች።
የGwen Ifill የፕሬስ ነፃነት ሽልማት
የ2026 Gwen Ifill Press Freedom Award የኤል ሳልቫዶር ጋዜጠኛና El Faro መስራች ካርሎስ ዳዳ ተሸላሚ ሆኗል።
ዳዳ ለዓመታት በሙስና፣ በወንጀለኛ ቡድኖች፣ በሰብዓዊ መብቶች ጥሰትና በመንግሥት አሰራር ላይ የምርመራ ዘገባዎችን በማቅረብ የሚታወቅ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት ከመንግሥታዊ ጫና የተነሳ በስደት እየኖረ ነው።
CPJ እንደገለጸው፣ የ2026 ተሸላሚዎች የተመረጡት ከፍተኛ አደጋና ጫና ውስጥ ሆነው ለሕዝብ እውነታን ለማድረስ ባሳዩት ድፍረትና ቁርጠኝነት መሠረት ነው።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#ethiopia | የጋዜጠኞችን ጥበቃ ኮሚቴ (CPJ) ለ36ኛ ጊዜ የሚያዘጋጀውን ዓመታዊ International Press Freedom Awards (IPFA) የ2026 ተሸላሚ ጋዜጠኞችን ይፋ አድርጓል።
የሽልማት ሥነ ሥርዓቱ ኅዳር 19 ቀን 2026 በኒውዮርክ ከተማ የሚካሄድ ሲሆን፣ ከተለያዩ አገራት የተውጣጡ ጋዜጠኞች በድፍረታቸውና በሙያዊ ተግባራቸው ይሸለማሉ።
በዚህ ዓመት ከተሸለሙት መካከል ከሊባኖስ፣ ከኤርትራ፣ ከሀንጋሪ፣ ከኮሎምቢያ እና ከሚያንማር የመጡ ጋዜጠኞች ይገኛሉ።
ክርስቲና አሲ – ሊባኖስ
የAFP ፎቶ ጋዜጠኛ ክርስቲና አሲ በጥቅምት 2023 በእስራኤል–ሊባኖስ ድንበር ዘገባ ስትሰራ በደረሰባት ጥቃት ቀኝ እግሯን አጥታለች፤ የሮይተርስ ጋዜጠኛ ኢሳም አብዳላህም በዚያው ጥቃት ተገድሏል።
CPJ እንደሚለው፣ በዚህ ጉዳይ እስካሁን ተጠያቂ የሆነ አካል የለም። አሲ ከዚያ በኋላ ለጋዜጠኞች ደኅንነትና ለፍትሕ ድምፅ ሆና እየሠራች ነው።
"ኤርትራ 16"
CPJ በዚህ ዓመት ለ25 ዓመታት ያለ ፍርድ ታስረው የቆዩትን "ኤርትራ 16" የተባሉ 16 ጋዜጠኞች በጋራ ሸልሟል።
እነዚህ ጋዜጠኞች በ2001 የግል ሚዲያዎች ከተዘጉ በኋላ ታስረው ሲሆን፣ እስካሁን ክስ አልቀረበባቸውም፣ ፍርድ ቤትም አልቀረቡም። የጤናቸውና የሕይወታቸው ሁኔታ እንኳን በግልፅ አይታወቅም።
ሳቦልች ፓንዪ – ሀንጋሪ
የምርመራ ጋዜጠኛው ሳቦልች ፓንዪ የሩሲያ ተፅዕኖ፣ ሙስናና የፖለቲካ ሥልጣን ላይ በሠራቸው ዘገባዎች የሚታወቅ ሲሆን፣ በ2026 የሀንጋሪ ምርጫ ዋዜማ ከባድ ጫናና የስለላ ክስ ተጋፍጦበታል።
ኤስቴፋኒ ሮድሪጌዝ – ኮሎምቢያ
በአሜሪካ የስፓኒሽ ቋንቋ ሚዲያ Nashville Noticias ዘጋቢ የሆነችው ኤስቴፋኒ ሮድሪጌዝ በ2026 በICE ተይዛ ታስራ ነበር።
CPJ ጉዳዩ በስደተኞች ጉዳይ ላይ በምታደርገው ዘገባ ምክንያት በጋዜጠኞች ላይ የሚደረግ ጫናን የሚያሳይ ነው ብሏል።
ሳይ ዛው ታይክ – ሚያንማር
የMyanmar Now ፎቶ ጋዜጠኛ ሳይ ዛው ታይክ በ2023 የCyclone Mocha ጉዳትን ሲዘግብ ተይዞ 20 ዓመት ከባድ እስራት ተፈርዶበታል።
CPJ እንደሚለው ሚያንማር በዓለም ላይ ጋዜጠኞችን በእስር ከሚያቆዩ አገራት መካከል ሁለተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች።
የGwen Ifill የፕሬስ ነፃነት ሽልማት
የ2026 Gwen Ifill Press Freedom Award የኤል ሳልቫዶር ጋዜጠኛና El Faro መስራች ካርሎስ ዳዳ ተሸላሚ ሆኗል።
ዳዳ ለዓመታት በሙስና፣ በወንጀለኛ ቡድኖች፣ በሰብዓዊ መብቶች ጥሰትና በመንግሥት አሰራር ላይ የምርመራ ዘገባዎችን በማቅረብ የሚታወቅ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት ከመንግሥታዊ ጫና የተነሳ በስደት እየኖረ ነው።
CPJ እንደገለጸው፣ የ2026 ተሸላሚዎች የተመረጡት ከፍተኛ አደጋና ጫና ውስጥ ሆነው ለሕዝብ እውነታን ለማድረስ ባሳዩት ድፍረትና ቁርጠኝነት መሠረት ነው።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
16 hours ago
በሀገር ውስጥ አቅም ውስብስብ የልብ ቀዶ ጥገናን በተሳካ ሁኔታ ማካሄድ መቻሉ ተገለፀ
****************
በኢትዮጵያ የልብ ሕሙማን ሕፃናት መርጃ ለሁለት ሕፃናት ህይወታቸውን የሚታደግ ውስብስብ የልብ ቀዶ ጥገና በተሳካ ሁኔታ ማካሄዱን ገለፀ።
ቀዶ ጥገናው የተደረገው ለ6 ዓመት እና ለ8 ወር ሕፃናት ሲሆን፣ ከቀዶ ጥገና ህክምናው በኋላ የህጻናቱ ጤንነት በመልካም ሁኔታ ላይ እንደሚገኝ ተገልጿል።
ህክምናውን በዶክተር ፍፁም አርጋው የሚመራ የሀገር ውስጥ የልብ ቀዶ ጥገና ቡድን የመራው ሲሆን፣ በዶክተር ሜሮን ተስፋዬ የሚመራው የፅኑ ህክምና ቡድንም ለህፃናቱ ማገገሚያ የሚሆን ልዩ ክትትል እያደረገ መሆኑን ከማዕከሉ ያገኘነው መረጃ አመልክቷል።
እንዲህ ያሉ ውስብስብ የልብ ቀዶ ጥገናዎች በሀገር ውስጥ መከናወናቸው የህፃናትን ሕይወት ከመታደግ ባለፈ የሀገሪቱን የልብ ሕክምና አቅም እየጎለበተ ስለመሆኑ የሚያሳይ ነው ተብሏል።
በኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት ከ7,000 በላይ ታካሚ ሕፃናት የልብ ቀዶ ጥገና ለማግኘት በረጅም የተጠባባቂነት ሰልፍ ላይ ይገኛሉ።
እንደዚህ ያሉ ውስብስብ ቀዶ ጥገናዎች በውጭ ሀገራት ለማካሄድ እስከ ሺዎች ዶላር የሚጠይቁ በመሆናቸው፣ ማዕከሉ በነጻ የሚሰጠው ይህ አገልግሎት ለታካሚ ቤተሰቦች ከፍተኛ የፋይናንስ እፎይታን ሰጥቷል።
ከዚህም በላይ የውጭ ሀገር የበጎ አድራጎት ቡድኖችን ሳይጠብቁ በሀገር ውስጥ የልብ ስፔሻሊስቶች አቅም ብቻ መከናወኑ ኢትዮጵያ በዘርፉ ያላትን የሕክምናና የቴክኖሎጂ አቅም ወደ አዲስ ደረጃ ማሸጋገሯን ማሳያ መሆኑ ተጠቅሷል።
በኢንቲሀድ አብራር
****************
በኢትዮጵያ የልብ ሕሙማን ሕፃናት መርጃ ለሁለት ሕፃናት ህይወታቸውን የሚታደግ ውስብስብ የልብ ቀዶ ጥገና በተሳካ ሁኔታ ማካሄዱን ገለፀ።
ቀዶ ጥገናው የተደረገው ለ6 ዓመት እና ለ8 ወር ሕፃናት ሲሆን፣ ከቀዶ ጥገና ህክምናው በኋላ የህጻናቱ ጤንነት በመልካም ሁኔታ ላይ እንደሚገኝ ተገልጿል።
ህክምናውን በዶክተር ፍፁም አርጋው የሚመራ የሀገር ውስጥ የልብ ቀዶ ጥገና ቡድን የመራው ሲሆን፣ በዶክተር ሜሮን ተስፋዬ የሚመራው የፅኑ ህክምና ቡድንም ለህፃናቱ ማገገሚያ የሚሆን ልዩ ክትትል እያደረገ መሆኑን ከማዕከሉ ያገኘነው መረጃ አመልክቷል።
እንዲህ ያሉ ውስብስብ የልብ ቀዶ ጥገናዎች በሀገር ውስጥ መከናወናቸው የህፃናትን ሕይወት ከመታደግ ባለፈ የሀገሪቱን የልብ ሕክምና አቅም እየጎለበተ ስለመሆኑ የሚያሳይ ነው ተብሏል።
በኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት ከ7,000 በላይ ታካሚ ሕፃናት የልብ ቀዶ ጥገና ለማግኘት በረጅም የተጠባባቂነት ሰልፍ ላይ ይገኛሉ።
እንደዚህ ያሉ ውስብስብ ቀዶ ጥገናዎች በውጭ ሀገራት ለማካሄድ እስከ ሺዎች ዶላር የሚጠይቁ በመሆናቸው፣ ማዕከሉ በነጻ የሚሰጠው ይህ አገልግሎት ለታካሚ ቤተሰቦች ከፍተኛ የፋይናንስ እፎይታን ሰጥቷል።
ከዚህም በላይ የውጭ ሀገር የበጎ አድራጎት ቡድኖችን ሳይጠብቁ በሀገር ውስጥ የልብ ስፔሻሊስቶች አቅም ብቻ መከናወኑ ኢትዮጵያ በዘርፉ ያላትን የሕክምናና የቴክኖሎጂ አቅም ወደ አዲስ ደረጃ ማሸጋገሯን ማሳያ መሆኑ ተጠቅሷል።
በኢንቲሀድ አብራር
19 hours ago
የጥገና ሥራ ለማከናወን የሚቋረጥ የኃይል አቅርቦት
ሐምሌ 30 ቀን 2018 ዓ.ም የጥገና ሥራ ለማከናወን የኃይል አቅርቦት የሚቋረጥባቸው አካባቢዎች
✅ከጠዋቱ 4፡00-11፡00
👉ኮተቤ፣ መሪ፣ አያት አደባባይ፣ ሲቪል ሰርቪስ፣ መሪ ሚካኤል፣ ተ/ብርሃን አምባዬ፣ ቡራዩ መስጊድ እና አካባቢው፣
👉ሪፍት ቫሊ ዩኒቨርሲቲ ፣ ፀርሐ ፅዮን ቤ/ክ ፣ ቡራዩ ወለጋ ሰፈር፣ ድሬ ከአስፋልት በታች፣ ጉዳ፣ ኬላ፣ ጉዮ እና አካባቢው፣
👉ታጠቅ ኢንዱስትሪ መንደር በከፊል፣ቶልቻ፣ድሬ ከአስፋልት በላይ፣ ገፈርሳ ውሀ ግድብ፣ ሲሊ፣ ከረላ፣ መናገሻ እና አካባቢው፣
✅ከጠዋቱ 2፡00-10፡30
👉ለገጣፎ ባጫ ሞል፣ሚካኤል ቤ/ክ፣ የካአባዶ፣ ኮዬ ፈጬ እና አካባቢው፣
✅ከጠዋቱ 3፡00-10፡00
👉10 ኪሎ በከፊል፣ ዶሮ እርባታ ፣ ቀንብሬ፣ አፍሪካ ልሕቀት ማዕከል፣ አርኪ ውሃ፣ ሱሉልታ መሐል ከተማ፣ ለገዲማ ፣ ጫንጮ አቢሲኒያ እና አካባቢው፣
👉ሲሚንቶ፣ ሳሊተ ምሕረት ቤ/ክ ፣ ጆርጅ ዘይት ቤት፣ ሜታ ቢራ አካባቢ አካባቢው የኤሌክትሪክ ኃይል ይቋረጣል።
ስለሆነም በአካባቢው የምትገኙ ክቡራን ደንበኞቻችን ይህንኑ በመገንዘብ ከወዲሁ ተገቢውን ቅድመ ዝግጅት እንድታደርጉ እናሳውቃለን።
#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት
Seledadotio
Seledadotio
ሐምሌ 30 ቀን 2018 ዓ.ም የጥገና ሥራ ለማከናወን የኃይል አቅርቦት የሚቋረጥባቸው አካባቢዎች
✅ከጠዋቱ 4፡00-11፡00
👉ኮተቤ፣ መሪ፣ አያት አደባባይ፣ ሲቪል ሰርቪስ፣ መሪ ሚካኤል፣ ተ/ብርሃን አምባዬ፣ ቡራዩ መስጊድ እና አካባቢው፣
👉ሪፍት ቫሊ ዩኒቨርሲቲ ፣ ፀርሐ ፅዮን ቤ/ክ ፣ ቡራዩ ወለጋ ሰፈር፣ ድሬ ከአስፋልት በታች፣ ጉዳ፣ ኬላ፣ ጉዮ እና አካባቢው፣
👉ታጠቅ ኢንዱስትሪ መንደር በከፊል፣ቶልቻ፣ድሬ ከአስፋልት በላይ፣ ገፈርሳ ውሀ ግድብ፣ ሲሊ፣ ከረላ፣ መናገሻ እና አካባቢው፣
✅ከጠዋቱ 2፡00-10፡30
👉ለገጣፎ ባጫ ሞል፣ሚካኤል ቤ/ክ፣ የካአባዶ፣ ኮዬ ፈጬ እና አካባቢው፣
✅ከጠዋቱ 3፡00-10፡00
👉10 ኪሎ በከፊል፣ ዶሮ እርባታ ፣ ቀንብሬ፣ አፍሪካ ልሕቀት ማዕከል፣ አርኪ ውሃ፣ ሱሉልታ መሐል ከተማ፣ ለገዲማ ፣ ጫንጮ አቢሲኒያ እና አካባቢው፣
👉ሲሚንቶ፣ ሳሊተ ምሕረት ቤ/ክ ፣ ጆርጅ ዘይት ቤት፣ ሜታ ቢራ አካባቢ አካባቢው የኤሌክትሪክ ኃይል ይቋረጣል።
ስለሆነም በአካባቢው የምትገኙ ክቡራን ደንበኞቻችን ይህንኑ በመገንዘብ ከወዲሁ ተገቢውን ቅድመ ዝግጅት እንድታደርጉ እናሳውቃለን።
#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት
Seledadotio
Seledadotio
20 hours ago
በመዲናዋ የደረጃ “ለ” ግብር ከፋዮች የግብር ጫና እንዳይደርስባቸው እየተሰራ ነው
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ በመዲናዋ በአነስተኛ የንግድ ስራ ላይ የተሰማሩ የደረጃ “ለ” ግብር ከፋዮች እንዲበረታቱ፣ የግብር ጫና እንዳይደርስባቸውና ትርፋማነታቸውን በማጎልበት ወደ ቀጣይ ደረጃ እንዲሸጋገሩ በቁርጠኛነት እየሰራሁ ነው አለ።
ቢሮው በደረጃ “ለ” ግብር ከፋዮች አከፋፈል በሚነሱ ጥያቄዎችና ቅሬታዎች አፈታት ዙሪያ በሰጠው መግለጫ፤ ባለፉት ሁለት ዓመታት ሰፋፊ የሪፎርም ተግባራት ተከናውነዋል።
የሪፎርም ተግባራቱ ፍትሐዊ የግብር አሰባሰብ ስርዓት መዘርጋት፣ የመልካም አስተዳደር እና የአገልግሎት አሰጣጥ እንዲሁም የሌብነትና ብልሹ አሰራሮችን መቅረፍ የሚያስችሉ መሆናቸው ተጠቁሟል፡፡
የ2018 የግብር ዘመን የደረጃ “ለ” ግብር ከፋዮች አብዛኞቹ በኦንላይን የክፍያ ስርዓት ግብራቸውን መክፈላቸውና የተቀሩትም እየከፈሉ መሆኑ ተመላክቷል።
በከተማዋ በተለያዩ የንግድ ዘርፎች የተሰማሩ 456 ሺህ 433 የደረጃ “ለ” ግብር ከፋዮች እንደሚገኙና ከእነዚህ ግብር ከፋዮችም 9 ነጥብ 2 ቢሊየን ብር ለመሰብሰብ መታቀዱም ተገልጿል።
የደረጃ “ለ” ነጋዴዎች ግብር ከተቀጣሪዎች ያነሰ መሆኑና ይህም የሆነው የከተማ አስተዳደሩ አነስተኛ ነጋዴዎችን ለማበረታታትና ለማሳደግ ባለው ቁርጠኝነት ምክንያት እንደሆነ መግለጫው አመላክቷል።
እስከ ሐምሌ 25 መልእክት የደረሳችሁ ግብር ከፋዮች እስከ ሐምሌ 30 ቀን 2018 ዓ.ም በኦንላይን እንድትከፍሉ፣ መልእክት ያልደረሳችሁ ወይም ከሐምሌ 25 በኋላ የደረሳችሁ ደግሞ ያለቅጣት እስከ ነሐሴ 20 ቀን 2018 ዓ.ም መክፈል ስለምትችሉ በትዕግስት እንድትጠባበቁ ሲልም ቢሮው አሳስቧል።
ግብር በዛብኝ የሚል ቅሬታ ላለው ማንኛውም ግብር ከፋይ የቅሬታ አፈታት ስርዓት ተዘርግቶ ወደ ተግባር የተገባ መሆኑንም ጠቁሟል።
በስልክ የጽሁፍ መልዕክት የተላከው የደረጃ “ለ” ዓመታዊ ግብር፣ ግብር ከፋዮች በቅድመ ታክስ የከፈሉትን ገንዘብ ተቀናሽ አድርጎ የያዘ እንደሆነም ተገልጿል።
በአዲስ አበባ ከተማ በ2019 በጀት ዓመት 502 ነጥብ 27 ቢሊየን፣ በገቢዎች ቢሮ 380 ቢሊየን ብር ገቢን በፍትሐዊነት ለመሠብሰብ መታቀዱም ተጠቁሟል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ በመዲናዋ በአነስተኛ የንግድ ስራ ላይ የተሰማሩ የደረጃ “ለ” ግብር ከፋዮች እንዲበረታቱ፣ የግብር ጫና እንዳይደርስባቸውና ትርፋማነታቸውን በማጎልበት ወደ ቀጣይ ደረጃ እንዲሸጋገሩ በቁርጠኛነት እየሰራሁ ነው አለ።
ቢሮው በደረጃ “ለ” ግብር ከፋዮች አከፋፈል በሚነሱ ጥያቄዎችና ቅሬታዎች አፈታት ዙሪያ በሰጠው መግለጫ፤ ባለፉት ሁለት ዓመታት ሰፋፊ የሪፎርም ተግባራት ተከናውነዋል።
የሪፎርም ተግባራቱ ፍትሐዊ የግብር አሰባሰብ ስርዓት መዘርጋት፣ የመልካም አስተዳደር እና የአገልግሎት አሰጣጥ እንዲሁም የሌብነትና ብልሹ አሰራሮችን መቅረፍ የሚያስችሉ መሆናቸው ተጠቁሟል፡፡
የ2018 የግብር ዘመን የደረጃ “ለ” ግብር ከፋዮች አብዛኞቹ በኦንላይን የክፍያ ስርዓት ግብራቸውን መክፈላቸውና የተቀሩትም እየከፈሉ መሆኑ ተመላክቷል።
በከተማዋ በተለያዩ የንግድ ዘርፎች የተሰማሩ 456 ሺህ 433 የደረጃ “ለ” ግብር ከፋዮች እንደሚገኙና ከእነዚህ ግብር ከፋዮችም 9 ነጥብ 2 ቢሊየን ብር ለመሰብሰብ መታቀዱም ተገልጿል።
የደረጃ “ለ” ነጋዴዎች ግብር ከተቀጣሪዎች ያነሰ መሆኑና ይህም የሆነው የከተማ አስተዳደሩ አነስተኛ ነጋዴዎችን ለማበረታታትና ለማሳደግ ባለው ቁርጠኝነት ምክንያት እንደሆነ መግለጫው አመላክቷል።
እስከ ሐምሌ 25 መልእክት የደረሳችሁ ግብር ከፋዮች እስከ ሐምሌ 30 ቀን 2018 ዓ.ም በኦንላይን እንድትከፍሉ፣ መልእክት ያልደረሳችሁ ወይም ከሐምሌ 25 በኋላ የደረሳችሁ ደግሞ ያለቅጣት እስከ ነሐሴ 20 ቀን 2018 ዓ.ም መክፈል ስለምትችሉ በትዕግስት እንድትጠባበቁ ሲልም ቢሮው አሳስቧል።
ግብር በዛብኝ የሚል ቅሬታ ላለው ማንኛውም ግብር ከፋይ የቅሬታ አፈታት ስርዓት ተዘርግቶ ወደ ተግባር የተገባ መሆኑንም ጠቁሟል።
በስልክ የጽሁፍ መልዕክት የተላከው የደረጃ “ለ” ዓመታዊ ግብር፣ ግብር ከፋዮች በቅድመ ታክስ የከፈሉትን ገንዘብ ተቀናሽ አድርጎ የያዘ እንደሆነም ተገልጿል።
በአዲስ አበባ ከተማ በ2019 በጀት ዓመት 502 ነጥብ 27 ቢሊየን፣ በገቢዎች ቢሮ 380 ቢሊየን ብር ገቢን በፍትሐዊነት ለመሠብሰብ መታቀዱም ተጠቁሟል።
1 day ago
ከ1 ሚሊዮን ብር በላይ የሚያወጣ ንብረት የሰረቀው የሆስፒታሉ ጥበቃ በ7 ዓመት ጽኑ እስራት ተቀጣ
ተከሳሽ እንድሪያስ ቶማስ ግያ በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ማስተማሪና ሪፈራል ሆስፒታል የጥበቃ ሠራተኛ ሆኖ እየሰራ ሀምሌ 22 ቀን 2018 ከምሽቱ 4:00 እስከ 6፡00 ባለዉ ጊዜ የወንጀል ድርጊቱ ተፈፅሟል።
የሆስፒታሉ ንብረት የሆነውን ሶስት ማይክሮስኮፕ የእያንዳንዳቸዉ ዋጋ ሶስት መቶ ሀምሳ ሺ ብር በድምሩ አንድ ሚሊዮን ሀምሳ ሺ ብር የሚያወጣዉን ከክፍሉ ሠራተኞች ጋር በመተባበር ንብረቱ ያለበትን ክፍል በቁልፍ ከፍቶ ከወሰደ እና ንብረቱን በተቋሙ ዉስጥ ባለዉ ሳርና ሀረግ ዉስጥ ደብቆ ካቆየ በኋላ ሀምሌ 25 ከሌሊቱ 9 ሰዓት ንብረቱን ካቆየበት ሥፍራ አንስቶ እየወሰደ እያለ ከንብረቱ ጋር የተያዘ ስለሆነ ተከሳሽ በፈፀመው ከባድ ስርቆት ወንጀል ተከሷል ።
የወላይታ ሶዶ ከተማ አስተዳደር ፍትህ መምሪያ ዐ/ሕግ ያቀረበውን ክስ ሲያከራክር የቆየው የወላይታ ሶዶ ከተማ አስተዳደር ከፍተኛ ፍርድ ቤት ተከሳሽ የቀረበበትን ክስ ሙሉ በሙሉ ያመነ መሆኑን ግምት ውስጥ በማስገባት የጥፋተኝነት ውሳኔ ሰጥቷል። ተከሳሽ የቀረበበትን ክስ ያመነ መሆኑን፣ የቤተሰብ አስተዳደር እንዲሁም ቀደም ስል የወንጀል ሪከርድ የሌለበት መሆኑን ግምት ውስጥ በማስገባት በ7 አመት ጽኑ እስራት እንድቀጣ ውሳኔ አሳልፎል።
የተሰረቀው ከአንድ ሚሊዮን በላይ ዋጋ የሚያወጣው ማይክሮስኮፕ ለኦቶና ሪፌራል ሆስፒታል ተመላሽ መደረጉን የወላይታ ሶዶ ከተማ አስተዳደር ከፍተኛ ፍርድ ቤት ኮሚኒኬሽን አስታውቋል።
Seledadotio
Seledadotio
ተከሳሽ እንድሪያስ ቶማስ ግያ በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ማስተማሪና ሪፈራል ሆስፒታል የጥበቃ ሠራተኛ ሆኖ እየሰራ ሀምሌ 22 ቀን 2018 ከምሽቱ 4:00 እስከ 6፡00 ባለዉ ጊዜ የወንጀል ድርጊቱ ተፈፅሟል።
የሆስፒታሉ ንብረት የሆነውን ሶስት ማይክሮስኮፕ የእያንዳንዳቸዉ ዋጋ ሶስት መቶ ሀምሳ ሺ ብር በድምሩ አንድ ሚሊዮን ሀምሳ ሺ ብር የሚያወጣዉን ከክፍሉ ሠራተኞች ጋር በመተባበር ንብረቱ ያለበትን ክፍል በቁልፍ ከፍቶ ከወሰደ እና ንብረቱን በተቋሙ ዉስጥ ባለዉ ሳርና ሀረግ ዉስጥ ደብቆ ካቆየ በኋላ ሀምሌ 25 ከሌሊቱ 9 ሰዓት ንብረቱን ካቆየበት ሥፍራ አንስቶ እየወሰደ እያለ ከንብረቱ ጋር የተያዘ ስለሆነ ተከሳሽ በፈፀመው ከባድ ስርቆት ወንጀል ተከሷል ።
የወላይታ ሶዶ ከተማ አስተዳደር ፍትህ መምሪያ ዐ/ሕግ ያቀረበውን ክስ ሲያከራክር የቆየው የወላይታ ሶዶ ከተማ አስተዳደር ከፍተኛ ፍርድ ቤት ተከሳሽ የቀረበበትን ክስ ሙሉ በሙሉ ያመነ መሆኑን ግምት ውስጥ በማስገባት የጥፋተኝነት ውሳኔ ሰጥቷል። ተከሳሽ የቀረበበትን ክስ ያመነ መሆኑን፣ የቤተሰብ አስተዳደር እንዲሁም ቀደም ስል የወንጀል ሪከርድ የሌለበት መሆኑን ግምት ውስጥ በማስገባት በ7 አመት ጽኑ እስራት እንድቀጣ ውሳኔ አሳልፎል።
የተሰረቀው ከአንድ ሚሊዮን በላይ ዋጋ የሚያወጣው ማይክሮስኮፕ ለኦቶና ሪፌራል ሆስፒታል ተመላሽ መደረጉን የወላይታ ሶዶ ከተማ አስተዳደር ከፍተኛ ፍርድ ቤት ኮሚኒኬሽን አስታውቋል።
Seledadotio
Seledadotio
1 day ago
መዝሙረ ሄላም ላይ የተደረገ አጭር ኂሳዊ ንባብ
ከቢኒያም አቡራ
#ethiopia | አዳም ረታ ታሪክን ከነገሥታት፣ ከመሪዎች፣ ማኅበረሰቡ ባበጀው ድልድል ውስጥ ‹ላዕላይ› ከሚባሉት ደረጃዎች አንጻር አያስመለክተንም። ታሪካዊ ከሚባሉ አጋጣሚዎች ውስጥ የተዘነጉትን ጥቃቅን የታሪክ ኹነተ-ደቂቅ (micro-events) ይመርጣል። ይወስዳል መንገድ ላይ … “ቀዳዳ” በተሰኘው ታሪክ ላይ ፍንዳታውን ከሚሞት ዘመድ፣ ከሚደነግጥ ለማኝ፣ ከሚሰነጠቅ የወፍ እንቁላል፣ ከሚፈስ የእናት ወተት ጋር Micro-Macro Connection በመፍጠር የትልቁ ቀዳዳ መፈጠርን ከሚጢጢዬ ሽንቁሮች ጋር ያስተሳስርልናል። እንዲህ ያሉ የኒው ሂስቶሪሲዝም ባሕሪያትን ከዚህ ቀደም ባሳተማቸው መጻሕፍቱ ውስጥ በተለያየ መጠን እናገኛለን።
Adam Reta አዳም ረታ "መዝሙረ ሄላም" በተሰኘው በዐዲሱ መጽሐፉ ላይም በኢትዮጵያ ታሪካዊ-ፖለቲካዊ አጋጣሚ ውስጥ እንደ ዐውራ የሚታዩትን የእድገት በኅብረት ዘመቻን እንደነ-አሮን፣ እንደነቃል … ባሉ ገጸባሕርያት በኩል፣ የሰባ ሰባቱን ድርቅ በሄላም ጡት በኩል፣ “ጥላሁን ለምን ለምን ሞተ” እየተባለ ኢዮቤልዩ ቤተመንግሥት ጋር የተደረገውን ሰላማዊ ሰልፍ በሡልጣን በኩል፣ የከተማ መሬት ዐዋጅን በተለያዩ ግለሰቦች በኩል … እናያለን። በዚህም የታሪክን ትልቅ ካርታ ለመረዳት የተረሱና የጠለሉ ታሪኮችን ይመረምራል። ስለዚህ ነቁጣዊ ማኅበራዊ ክስተቶችን ወደ ታሪክ ምኩራብ በማምጣት ከትልቁ የታሪክ ምሥል ጎን ያስተያያል። ይህ ደግሞ የኒው ሂስቶሪሲዝም ኹነኛ ማጠንጠኛ ነው።
ልክ “ይወስዳል መንገድ ያመጣል መንገድ …” በተሰኘው መጽሐፉ ውስጥ ባለው “የመንግሥቱ ጊዜ” በሚለው ድርሰት ውስጥ፣ ትልቁን “የታኅሣሥ ግርግር”ን እንደ መቼት አምጥቶ የተጻፈውና የተተኮረው ግን ኹነተ-ደቂቅ (micro-events) ላይ ነው። ስለግርማሜ ንዋይ፣ ስለኮሌኔል ወርቅነህ ገበየሁ፣ ሰለጄነራል ሙልጌታ ቡሊ አይደለም የሚያትተው። ስለአንድ ብላቴና ከእንቅልፍ መነሳት፣ ስለገበጣ ጨዋታ፣ ቤተክርስቲያን ውስጥ ሕፃናትን አሰብስቦ ‹ኪራላይሶን› የሚያስብል ካሕን፣ ስለመንደር ውስጥ ሐሜቶች፣ ስለግለሰቦች ፍርሃት፣ በአጋጣሚ ስላየው አስደናቂ አሞራ … ያወጋል። የታሪክ አጋጣሚ አምጥቶ በታሪክ ውስጥ ግለሰቦች ላይ ስለሚረብበው የታሪክ መንፈስ ያትታል። ልክ እንደዚሁ መዝሙረ ሄላም ላይም ጽሑፉ ታሪክን አያብራራም፤ ነገር ግን ታሪክ እንዴት በሰው ልብ ውስጥ እንደሚኖር ያሳያል። በዚህ ኹነተ-ደቂቅ (micro-event) ምክንያት በዘመኑ ላይ ያገነገነውን ባሕላዊ እምነትን፣ የሥልጣን መዋቅርን፣ የወል ግንዛቤን አጨንቁረን እንድንመለከት ያስችለናል።
ከመንግሥት ሼልፍ ላይ ሳይኾን ከግለሰብ ጀርባ ላይ የተወሰደው የአዳም የአጻጻፍ መንገድ ከኒው ሂስቶሪስዝም ጽንሰ-ሐሳቦች ጋር በአንድ መም ላይ የሚሄዱ ናቸው። መዝሙረ ሄላም የተሰኘው ዐዲሱ የአዳም ረታ መጽሐፍ የኒው ሂስቶሪሲዝም ባሕርያትን ይጋራል። አንዳንድ ነገሮችን በዓይን መመልከት ባይቻልም በግብሩ (ቁስ ላይ በሚያደርገው ግፊት) ግን ይታወቃል። በመዝሙረ ሄላም መጽሐፍ ውስጥም አንዳንድ ነገሮችን በቀጥታ ማየት ባንችልም ቅሉ እነርሱን የሚያሳይልንን ነገሮች ግን እንቃኛለን። ዘማች ወጣት ተማሪዎችን እናያለን፤ መንግሥትን፣ ሕግንና ኃይልን ግን በቀጥታ አንመለከትም። የተማከለ ኃይል አናይም ግን የገጸባሕርያቱ የፍርሃት ምንጭ ከተማከለ ኃይል ጋር የተያያዘ ቀጭን መስመር መኖሩን እናያለን። መንግሥትም ቢኾን በቀጥታ አይገባም፤ ነገር ግን ፍርሃት እንደ ሥርዓት ዘዋሪ (system driver) ይኾናል። እንደ ሚሸል ፉኮ አገላለጽ ኃይል ከተማከለ ሥርዓት የሚመነጭ ሳይኾን በየትኛውም ቦታና ጊዜ በፍርሃት፣ በልማድ፣ በንግግር … ሊከሰት የሚችል ሂደት አይደል?
መዝሙረ ሄላም ላይ ታሪክ እንደ “circulation of social energy” ቀርቧል። መዝሙረ ሄላም ላይ መረጃ ከመንግሥት አይመጣም፤ ከግለሰብ እንጂ። የከተማ መሬት ዐዋጅም ኾነ የተማሪዎች ዘመቻ በገጸባሕርያቱ ወሬ ውስጥ ነው የሚንቀረቀበው። ይህ የመረጃ ሥርዓት ኃይል ማን እንዳለው ማን እንደሌለው ያሳያል። እንግዲህ ይህ በፉኮኛ micro-power መኾኑ ነው። በመዝሙረ ሄላም ላይ ታሪክ እንደ ወሬ እንጂ እንደ ሰነድ አይቀርብም።
ወሬ የፍርሃት ቤንዚን ነው … ፍርሃት ደግሞ በዝምታ መሸበብን ይፈጥራል … የዝምታ አፈ-ሙቅ ደግሞ ኃይለኛው እንዳይታይ ያደርጋል … የተደራጀው ኃይል ጥፋትን ሊያደርስ ባሰበ ቁጥር የወሬ ቤንዚን ይጨምራል። ሰዎች በዕቅብተ-ንግግር ራሳቸውን ሲሸብቡ ደርዝ ያለው ሙግት ይኮሰምናል፣ ንግግር ሲጠፋ ያልታወቀ አደጋ ይከሰታል፣ ፍርሃትም ይጨምራል። ያልታወቀ አደጋ ደግሞ ከታወቀ አካል ይመጣል። ስለዚህ ጥንስሱ የሚጀምረው ከወሬ እንደኾነ ያስመለክተናል። አዳም በመዝሙረ ሄላም ላይ ታሪክን እንደ “circulation of social energy” ሲያቀርብ ፕሬዝዳንት፣ ጀነራል፣ ፕሮፌሰር የኾኑ ታሪክ ከላዕላይ ያስቀመጣቸው ሰዎች አያስፈልጉትም። በአንጻሩ ሄላም ለማን እንደሳመችው ተደርጎ ብርሃኔ ያስወራው ወሬ፣ የሄላም አባት ወታደር በመኾኑ ምክንያት በካሱ፣ በሄኖክ እናት የተነዛው ወሬ እና ሄላም ከሄኖክ ጋር የተቆራረጠችበት መንገድ እንዲሁም የሄላምን የጡት ወተት በተመለከተ የተነዛው ወሬን ይጠቀማል።
መዝሙረ ሄላምን ከድኅረ-ቅኝ-አገዛዝ የኂስ መንገድ አንጻር እንመልከተው።
እውን ቅኝ-ግዛት ተረት ኾኖ ቀርቷል? በፖለቲካ፣ በኢኮኖሚ፣ በሥነልቦና ረገድ የቅኝ አገዛዝ ዳናው ሙሉ ለሙሉ ጠፍቷል? አዳም በመዝሙረ ሄላም ጽሑፍ ውስጥ ከቅኝ-ግዛት በተወረሰ መዋቅር ምክንያት የተሰናከለን ሕይወት ሊያስመለክተን ይኾን?
“ከተሞች ከቅኝ ግዛት በኋላ ሁለት ዓይነት መልክ ይኖራቸዋል፤ ለጥቂቱ የተድላ፣ ለተቀረው ደግሞ የአሳር መንደር ይኾናሉ” ይላል ፍራንዝ ፋኖን። በመዝሙረ ሄላም ላይ እና “የቢሾፍቱ ልጆች ጥላሞት” የተሰኘው ድርሰት ላይም ይህንን ነው የምንመለከተው። “ይወስዳል መንገድ ያመጣል መንገድ …” በተሰኘው መጽሐፉ ውስጥ ካሉ ጽሑፎች መካከል “የቢሾፍቱ ልጆች ጥላ ሞት” አንዱ ነው። የቢሾፍቱ ልጆች ሆቴሉን ያዩታል፤ ግን አይገቡበትም። ሆቴሉ የሀገራቸው መሬት ላይ ነው፤ እነርሱ ግን ከሆቴሉ ውጭ ናቸው። መናፈሻው ውስጥ አንዲት የፈረንጅ ልጅ ጠግባ ለልጆቹ እንደ ውሻ ዳቦ ትወረውርላቸዋለች። አፈር ላይ የወደቀን ዳቦ አራግፈው ይመገባሉ። በገዛ ሐይቃቸው ዳር ላይ ናቸው፤ ሌሎች ግን በጀልባ እየተንሸራሸሩ ይንፈላሰሳሉ። ለፈረንጆቹ ያደረው ሞገስ የላንድሮቨር ተፈናጣጭ ኾኗል። ሌሎቹ ግን ከመኪናው ውጪ ናቸው። ሞገስ እንደ እነርሱ ሕጻን ቢኾንም ለፈረንጅ በማሸርገዱ የትምህርት ቤቱ ባለቤት ሲመስል ሌሎች ልጆች ግን በገዛ መምህራቸው ይብጠለጠላሉ። የቢሾፍቱ ልጆች፣ ነጻ በተባለች ሀገር እየኖሩ በቅኝ ግዛት ጥላ ይተዳደራሉ። የቢሾፍቱ ልጆች በገዛ መንደራቸው አካሉ በማይታይ የቅኝ ግዛት እጅ ይገፋሉ። ሞገስ አይናገርም፤ የሚናገርለት አለ። ልክ የቢሾፍቱ ልጆች ላይ በአንድ ከተማ ውስጥ ሁለት የከተማ ምሥል እንደምናገኘው ሁሉ “የስንብት ቀለማት” ላይም በአዲስ አበባ ውስጥ ሁለት የከተማ ምሥል እንመለከታለን። እንደ ዘድሬክ፣ ሳተርን፣ ከተስፋዬ ወደ አሸናፊ የተቀየሩ የድሎት ምሥሎች እና የእነምትክ ጉልት፣ የእትየ እልልታ የጉርሻ መሸጫ መስኮት ያሉ የእጦት ሥዕል እናገኛለን። መዝሙረ ሄላም ላይም እንዲህ ያለ በአንድ ከተማ ላይ የሁለት ምሥሎች አደባባይ እጀግ ብዙ ቦታ ይገኛል።
በሌላኛው የድኅረ-ቅኝ-ግዛት ኂስ (postcolonial criticism) መዝሙረ ሄላምን ስንመለከት መጀመሪያ ላይ “ፈረንጅ ሲያደንቀኝና ሲገረምብኝ የሰሙ የአገሬ ደነዞች በየተራ “ካላስ የኔ ጎሳ ናት” … እያሉ መሻማት ጀመሩ ትላለች - ሄላም። በኋላ ደግሞ በተነዛባት አጓጉል ወሬ … የሄላምን ጡት ንቀው፣ አንጓጥጠው፣ አባረዋት ሲያበቁ የፈረንጅ የዱቄት ወተትን ይመርጣሉ። ይህ በባሕላዊ ማንነትና በዘመናዊነት መካከል የሚዋልል ማኅበረሰብን ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ የድኅረ-ቅኝ-ግዛት አካል ነው። በሌሎቹ የአዳም ሥራዎች ውስጥ ድኅረ-ቅኝ-ግዛት አተያይ በቋንቋና በኪነ-ጥበብ ምርጫ ውስጥ እንዴት እንደሚንፀባረቅ ያሳያል። በመዝሙረ ሄላም ላይ ደግሞ ምዕራባዊው ዓለም ለአገር በቀል መፍትኼ-ሥራይ የሚሰጠው ዋጋ ዝቅተኛ መኾኑንና የኢኮኖሚ ብዝበዛው አሁንም በረቂቅ መንገድ መቀጠሉን ያሳያል። እዚህ ላይ ሥዕለማርያም የተባለችዋን ገጸባሕርይ እና በውጭ ሀገራት የተነዙ ወሬዎችን ስንጨማምር ደግሞ የበለጠ ብዙ ለማለት ያስችላል።
መዝሙረ ሄላም ላይ እጅግ ብዙ ማኅበረሰባዊ ኂስ እናገኛለን። ለአብነት ያህል አንድ ሁለቱን እንቃኝ።
“መዝሙረ ሄላም” ላይ ማኅበረሰቡ በችላ-ባይነት አልያም በኾን ተብሎነት ልጆቹን ምን ያህል ተጠቂ እንዳደረጋቸው የሚያሳይ መልክ ተንጸባርቆበታል ማለት ይቻላል። ጋሽ ክብካብና ዘመናይ ኾን ብለው ቴዲና ሄላም ላይ የሚያደርሱትን፣ ተክለማርያም የወላጁን(የዘሪቱን) ችላ-ባይነት ለአብነት ማቅረብ ይቻላል። ማኅበረሰቡ ልጆችን “የነገ ተስፋዎች” ይላል፤ ነገር ግን ዛሬያቸው ላይ አይሠራም።
ማኅበረሰብ የመማጸኛ ከተማዎችን ወደ ተጨማሪ ግፍ መሥሪያ ቦታዎች እንደሚቀይር በአዳም መጻሕፍት ላይ በብዛት እንመለከታለን። “ይወስዳል መንገድ …” ላይ … “ቀዳዳ” በተሰኘው ታሪክ ላይ ማርታ ለደበበ በምትሰጠው ፍቅር ሳቢያ የሚሠራበትን ግፍ የምታስረሳ ብትኾንም ማኅበረሰቡ ግን ተጨማሪ ግፍ የሚሠራበት መሣሪያ ኾናለች። የስንብት ቀለማት ላይ ምኒልክ ከዚያ ሁሉ እስርና እንግልት በኋላ፣ “በፊያሜታ አርፋለሁ” ብሎ ቤቷ ሲሄድ ተጨማሪ ሕመም በጆሮው በኩል ጭንቅላቱ ላይ ይሻጥበታል። መዝሙረ ሄላም ላይም፣ ሄላም “ሙዚቃዬን ከሕዝብ ጆሮ ያደርስልኛል … ያሳርፈኛል …” ብላ የተመካችበት ምናሴ እንጦሮጦስ ይጨምራታል። ማኅበረሰባችን የመስቀል ተ ሠላጢን ግብር እንዳለው፣ ከላይ አሳልሞ ከታች በአንካሴው ጉድጓድ እንደሚምስ ያሳያል። ይህም የመልእክትን ወጭት ሰብሮ የወጣ ጥበባዊ አጻጻፍ ነው። በፈጣጣው የቀረበ የትችት ኮሶ አይደለም። ድንቅ ነው!
መዝሙረ ሄላም ላይ ከምናገኛቸው ዋና ዋና ገጸባሕርያት የተወሰኑት (አሮን፣ ቃል፣ ምናሴ፣ ሄላም) ላይ መጠነኛ ቅኝት እናድርግ።
auto-fiction ዓይነት አጻጻፍ ባለው የአሮን አተራረክ ውስጥ አሮን “system observer” መኾኑን እንገነዘባለን። ሥርዓቱን ያያል፣ ዘማቹን ያስተውላል፣ ቃለጉባኤ ይይዛል፣ ችግሩን ይመለከታል፣ ይጽፋል። አሮን የተገፋ ታሪክ ድምፅ ነው፤ ንቃት አለው፣ ግን የታሪክ ሂደትን የሚቀይር ኃይል የለውም፤ ስለዚህም ያ ሁሉ የጻፈውን ጽሑፍን ያጣል። የንቃት ችግር የለበትም፤ የማኅበራዊ ንቃት ድምፅነቱን ከዘመነ አባት ጋር ባደረገው ውይይት ውስጥ ተመልክተናል። ግን ደግሞ ይህ ብቻውን የቆመ ነጠላ ነገር ነው፤ ምክንያቱም ማኅበራዊ ተሳትፎ የለበትም። ቃል የተሰኘችው ገጸባሕርይም እንደ አሮን ናት፤ ንቃት ያላት፣ system observer ናት። ማኅበራዊ ንቃት ማኅበራዊ እንቅስቃሴ ካላገዘው ግንጥል ጌጥ ነው። ቃልና አሮን ንቃት አላቸው፤ ግን ንቃታቸውን ተግባር አላገዘውም፤ ንቃቱን የሚተገብር አደረጃጀት የላቸውም። ስለዚህ ዕጣ-ፈንታቸው ውድቀት ይኾናል። በኢትዮጵያ ውስጥ የተንሰራፋውን ይህን የድግግሞሽ አዙሪት መዝሙረ ሄላም ላይ ደራሲ አዳም ረታ በሰላ ብዕር አስቀምጧል።
የደራሲና የአርታኢ ትስስር በተንጸባረቀበት በሄላም አተራረክ ውስጥ ምናሴ የተሰኘ ገጸባሕርይ እናገኛለን። ምናሴ የ-false collective consciousness ትእምርት ነው። ምናሴዎች ለሥልጣን ይሠራሉ፣ ራሳቸውን እንደ ነጻ ያስባሉ፤ ነገር ግን የሥርዓቱ የመጠቀሚያ መሣሪያ (system functionary) ናቸው። ምናሴዎች የኦልቪቴዎች ጥይት ናቸው። ምናሴዎች የሔላምዎች ስኬት ሳይኾን የገዛ ጥቅማቸውን የሚያስቀድሙ የማኅበረሰቡ አካል ናቸው። ምናሴ በሌላ መነጽር ብናየው የመንግሥት ቢሮክራት የመካከለኛው መደብ ውክል ነው። ሀገሩ ከንጉሣዊ ሥርዓት ወደ ወታደራዊ ሥርዓት ቢቀየርም፤ ከወታደራዊ ሥርዓት ወደ ሌላ ሥርዓት ቢለወጥም ምናሴያውያን ግን አይቀየሩም። ሥርዓት ይቀየራል - ምናሴያውያን አይቀየሩም፣ ትእዛዝ ይፈጽማሉ፣ ይከድራሉ። ይህ በኢትዮጵያ ፖለቲካል-ታሪክ ውስጥ የተደጋገመ፣ ግን ደግሞ ያልተስተዋለ እውነት ነው።
ሄላም የወታደር ልጅ ናት፤ እንዲያሳድጋት በአደራ የተሰጠው ቤተሰብ የሚበድላት። የሷ ዓይነት ዕጣ ከደረሰው እንደ ወንድሟ ከምታየው ቴዲ ከሚባል ልጅ ጋር ታድጋለች። መጀመሪያ የሚልዮን፣ የኋላ ኋላ የምናሴ ፍቅረኛ የምትኾን ድምፀ-መረዋ ሴት ናት። ሁሉ ነገሯን ባጣችበት ወቅት ጡቷ ተአምር ያመርታል።
በመዝሙረ ሄላም ላይ የሄላም የጡት ወተት የአንዳች ነገር ውክል ይመስለኛል። ሻዕቢያ ለታጋይ ወጣቶች ማሳደጊያ ፈልጓት ሊሰርቃት መፈለጉ በቀላሉ የሚዘለል ነገር ነው? ወተት እና ጡት በመጀመሪያ እይታ የሕፃናት ትዝታ፣ የእናትነት ምሥል፣ የእምነት እና የጾታ መነሳሳት የተዋሃዱበትም አይደል? ወተት ሕይወት ነው? የመጀመሪያ ምግብ፣ ከእናት ወደ ልጅ የሚፈስም አይደል? በክርስቲያናዊ ምልክት ንጹሕነትን አይወክልም? ወተት ከ“ቅዱስ” ወደ “ሥጋዊ” የሚያስተላልፍ ድልድይ ነው ማለት እንችል ይኾን? የሄላምን ጡት የጠባ ታማሚ ልጅ እንዴት ጤናማ ሊኾን ቻለ? የምን ትእምርት ነው? ሄላም ከብዙ ወንድ ጋር የወጣች እንደመኾኗ ለዚህ ሰናይ ግብር ለምን የሷ ጡት ተመረጠ?
ሌላው፣ መዝሙረ ሄላም ላይ ኦልቬቲን እናገኛታለን። ኦልቬቲ የግራጫ ቃጭልዋ። መዝገቡ ንፋስ መውጫ ሳለ፣ ባልንጀራው ኤልያስ የብልግና ሀሁ ሊያስተምረው እፊቱ ያቆማት ቀይ ሰሌዳ ነበረች ኦልቬቲ። መዝሙረ ሄላም ላይ ምናሴን እና ቤተሰቡን የምታሾር ዐውራ ገጸባሕርይ ኾና ትከሰታለች። መዝሙረ ሄላም እና ግራጫ ቃጭሎች በጋለሞታይቱ በኦልቬቲ ብቻ ሳይኾን በዘመነ እንድርያስ እና በመዝገቡ ዱባለም ይገናኛሉ። ነጋ ዳቦ ጋጋሪውም በ-typological space መዝሙረ ሄላም ላይ እናገኘዋለን።
መዝሙረ ሄላምን ከህላዌነት (Existentialism) አንጻር እንመልከተው። ሄላም ትርጉም በማይሰጥ ዓለም ውስጥ እንዴት እንደምትኖር እናነባለን። የሀገሯ ዳር ድንበር እንዳይነካ አባት ብታዋጣም አሳዳጊዎቿ ግን የወላጅን ፍቅር አዋጥተው አይለግሷትም። ወርቅ አበድራ ጠጠር ትነፈጋለች። ዕቃ ለማገዝ ቤቷ ድረስ ለመጣው ሚልዮን ልቧን ትሰጣለች። ሀና የሸነቆረችውን ክፍተት ለሞላችበት ውለታዋ ክፍያ ይኾን ዘንድ ሚልዮን ለሄላም የወለፈንዴ ቡጢ ያሳርፍባታል። ለሕይወት ትርጉም ለመስጠት ባስ ውስጥ ካገኘችው ሄኖክ ጋር ብትሞክርም የበለጠ የሕይወት ትርጉም ይዛባባታል። የወታደር ልጅ መኾኗ ሄላምነቷን በዜሮ ያባዘዋል። የመጨረሻው ስንብትም ከሄኖክ ጓደኛ አፎት በሚወጣ ሰይፍ መቀላት ይኾናል። ከሄኖክ ጓደኛ ጀርባ የሚውለበለበው ባንዲራ ደግሞ የሄኖክ ሸሚዝ መኾኑ ደግሞ ቁስሉን እንደ አቡሰዲቅ ያደርገዋል። ለሕይወቷ ትልቅ ትርጉም ያለውን የሙዚቃ ሥራዋን፣ “ትርጉም ወዳለው
ነገር ይቀይርልኛል” ብላ በምትተማመንበት በምናሴ ትነጠቃለች። ተአምር በሚያስብለው በጡት ወተት ምክንያት ለሕይወቷ ትርጉም ለመስጠት ትታትራለች። የጡት ወተቷን ምርምር በማድረግ ለትልቅ ዓለምአቀፍ በጎ ተፅዕኖ ታደርጋለች ተብላ የተቆጠረችው ሥዕለማርያም የዓለም አቀፍ መሳለቂያና ትችት ምንጭ ትኾንባታለች። ይህ ሁሉ ትርጉም የሌለው ድግግሞሽ ነው። ይህ ደግሞ በሳርተር የተገለጸውን “existence without essence”-ን ያሳያል።
የህላዌነት መሠረታዊ ሐሳብ ነጻነት ነው፤ ግን ነጻነት ፍርሃትን ይወልዳል። ሄላም ለአሮን ፍቅሯን መናገር ትችላለች፤ ነገር ግን ዝምታን መርጣለች። የግራጫው መዝገቡ፣ የእንጀራ እናቱ የምታደርስበትን በደል እንደሚያውቀው ሁሉ ሄላምም ክብካብና ዘበናይ የሚያደርሱባትን አድሎ ታውቃለች፤ ግን ለረዥም ጊዜ ዝም ብላለች። ሄላም፣ ሙዚቃዋን ካጣች በኋላ ወደ ባንዱ ሄዳ መጋፈጥ ትችላለች፤ ነገር ግን አትሄድም … ይህ በሳርተርኛ bad faith ነው።
የሄላም ምርጫ ዝምታ ኾነ እንጂ ደካማ ናት ማለት አይደለም። “አልተናገርኩም ማለት አላውቀውም ማለት አይደለም” የሚል ዝምታ ነው ያላት። በሌላ ጎኑ ደግሞ ዝምታዋ፣ የለመደችውን ግፍ ከማታውቀው ዐዲስ ግፍ የመምረጥ ኹኔታ ነው። ዐዳዲስ ግፎችን ለመሸሽ በዝምታ አላዋቂነት ዛጎል ውስጥ የመደበቅ ብቃት ነው። የለመደችውን ግፍ የመከላከል አቅም ስላላት ባለመደችው ግፍ እንዳያጠፏት ሠግታ በውስጣዊ ንቃተ ሕሊና የዘየደችው ብልሃት ሊኾን ይችላል። ዝምታዋ የመቆየቷ ምሥጢር ነው። ደበበ ቀዝቃዛ ገለልተኛ ነኝ የሚለው ሰው ለመኖር ሲል ሳይታወቀው ስሜቱን የሚቆጣጠርበት መንገድን ለማስታወስ ነው።
“የስንብት ቀለማት” ገጸባሕርይ የኾነው ዮሴፍም ብዙ ነገር ያውቃል፤ ግን ዝም ይላል … ፊያሜታ ቂል መስሏት ትዘባርቃለች … እሱ ግን “አልተናገርኩም ማለት አላውቀውም ማለት አይደለም” የሚል የዝምታ መልስ ይመልስላታል። እሷ ግን ዝምታው አይገባትም። የ“ቀዳዳ”ው ደበበ እና “የስንብት …” ዮሴፍ ቀዳዳውን አይሞሉትም፤ እያዩት ይኖራሉ። ዶነሮች ጥሩ ፈንድ ሲለቁ ፊያሜታ ፕሮጀክቱን ለአሳምነው ትሰጠውና ዮሴፍን “ምን ዶነሮች እኮ ጠፉ ትለዋለች” … ዝም ይላል፤ ይታዘባል።
ቃል መሣሪያ ነበር፤ በዘመነ ደበበ፣ በዘመነ ዮሴፍ፣ በዘመነ ሄላም እና በዘመነ መዝገቡ ዱባለ ግን ቃል አደገኛ ኾኗል፤ ዝምታ ኹነኛ መጠጊያ ነው … ይህ ከደርግ በኋላ የተፈጠረ “traumatized literary silence” ማሳያ ነው። ስለኾነም ተራኪዎቹ (ደበበ፣ መዝገቡ፣ ዮሴፍ እና ሄላም) ለምን ዝም አሉ ሳይኾን "ዝምታን የሚያመነጭ ሥርዓት ምን ይኾን?" ብለን እንድንጠይቅ ያደርጋል። ግለሰብ ዝም ሲል፤ ሕዝብ በጸጥታ ይዋጣል፤ የዚያኔ የተማከለው ኃይል አፍ ያወጣል።
የአዳምን ዐዲሱን መጽሐፍ "በንባብ ይለቅ" ብለን መርቀናል።
ቢኒያም አቡራ
ሐምሌ 25 / 2018 ዓ.ም
ከቢኒያም አቡራ
#ethiopia | አዳም ረታ ታሪክን ከነገሥታት፣ ከመሪዎች፣ ማኅበረሰቡ ባበጀው ድልድል ውስጥ ‹ላዕላይ› ከሚባሉት ደረጃዎች አንጻር አያስመለክተንም። ታሪካዊ ከሚባሉ አጋጣሚዎች ውስጥ የተዘነጉትን ጥቃቅን የታሪክ ኹነተ-ደቂቅ (micro-events) ይመርጣል። ይወስዳል መንገድ ላይ … “ቀዳዳ” በተሰኘው ታሪክ ላይ ፍንዳታውን ከሚሞት ዘመድ፣ ከሚደነግጥ ለማኝ፣ ከሚሰነጠቅ የወፍ እንቁላል፣ ከሚፈስ የእናት ወተት ጋር Micro-Macro Connection በመፍጠር የትልቁ ቀዳዳ መፈጠርን ከሚጢጢዬ ሽንቁሮች ጋር ያስተሳስርልናል። እንዲህ ያሉ የኒው ሂስቶሪሲዝም ባሕሪያትን ከዚህ ቀደም ባሳተማቸው መጻሕፍቱ ውስጥ በተለያየ መጠን እናገኛለን።
Adam Reta አዳም ረታ "መዝሙረ ሄላም" በተሰኘው በዐዲሱ መጽሐፉ ላይም በኢትዮጵያ ታሪካዊ-ፖለቲካዊ አጋጣሚ ውስጥ እንደ ዐውራ የሚታዩትን የእድገት በኅብረት ዘመቻን እንደነ-አሮን፣ እንደነቃል … ባሉ ገጸባሕርያት በኩል፣ የሰባ ሰባቱን ድርቅ በሄላም ጡት በኩል፣ “ጥላሁን ለምን ለምን ሞተ” እየተባለ ኢዮቤልዩ ቤተመንግሥት ጋር የተደረገውን ሰላማዊ ሰልፍ በሡልጣን በኩል፣ የከተማ መሬት ዐዋጅን በተለያዩ ግለሰቦች በኩል … እናያለን። በዚህም የታሪክን ትልቅ ካርታ ለመረዳት የተረሱና የጠለሉ ታሪኮችን ይመረምራል። ስለዚህ ነቁጣዊ ማኅበራዊ ክስተቶችን ወደ ታሪክ ምኩራብ በማምጣት ከትልቁ የታሪክ ምሥል ጎን ያስተያያል። ይህ ደግሞ የኒው ሂስቶሪሲዝም ኹነኛ ማጠንጠኛ ነው።
ልክ “ይወስዳል መንገድ ያመጣል መንገድ …” በተሰኘው መጽሐፉ ውስጥ ባለው “የመንግሥቱ ጊዜ” በሚለው ድርሰት ውስጥ፣ ትልቁን “የታኅሣሥ ግርግር”ን እንደ መቼት አምጥቶ የተጻፈውና የተተኮረው ግን ኹነተ-ደቂቅ (micro-events) ላይ ነው። ስለግርማሜ ንዋይ፣ ስለኮሌኔል ወርቅነህ ገበየሁ፣ ሰለጄነራል ሙልጌታ ቡሊ አይደለም የሚያትተው። ስለአንድ ብላቴና ከእንቅልፍ መነሳት፣ ስለገበጣ ጨዋታ፣ ቤተክርስቲያን ውስጥ ሕፃናትን አሰብስቦ ‹ኪራላይሶን› የሚያስብል ካሕን፣ ስለመንደር ውስጥ ሐሜቶች፣ ስለግለሰቦች ፍርሃት፣ በአጋጣሚ ስላየው አስደናቂ አሞራ … ያወጋል። የታሪክ አጋጣሚ አምጥቶ በታሪክ ውስጥ ግለሰቦች ላይ ስለሚረብበው የታሪክ መንፈስ ያትታል። ልክ እንደዚሁ መዝሙረ ሄላም ላይም ጽሑፉ ታሪክን አያብራራም፤ ነገር ግን ታሪክ እንዴት በሰው ልብ ውስጥ እንደሚኖር ያሳያል። በዚህ ኹነተ-ደቂቅ (micro-event) ምክንያት በዘመኑ ላይ ያገነገነውን ባሕላዊ እምነትን፣ የሥልጣን መዋቅርን፣ የወል ግንዛቤን አጨንቁረን እንድንመለከት ያስችለናል።
ከመንግሥት ሼልፍ ላይ ሳይኾን ከግለሰብ ጀርባ ላይ የተወሰደው የአዳም የአጻጻፍ መንገድ ከኒው ሂስቶሪስዝም ጽንሰ-ሐሳቦች ጋር በአንድ መም ላይ የሚሄዱ ናቸው። መዝሙረ ሄላም የተሰኘው ዐዲሱ የአዳም ረታ መጽሐፍ የኒው ሂስቶሪሲዝም ባሕርያትን ይጋራል። አንዳንድ ነገሮችን በዓይን መመልከት ባይቻልም በግብሩ (ቁስ ላይ በሚያደርገው ግፊት) ግን ይታወቃል። በመዝሙረ ሄላም መጽሐፍ ውስጥም አንዳንድ ነገሮችን በቀጥታ ማየት ባንችልም ቅሉ እነርሱን የሚያሳይልንን ነገሮች ግን እንቃኛለን። ዘማች ወጣት ተማሪዎችን እናያለን፤ መንግሥትን፣ ሕግንና ኃይልን ግን በቀጥታ አንመለከትም። የተማከለ ኃይል አናይም ግን የገጸባሕርያቱ የፍርሃት ምንጭ ከተማከለ ኃይል ጋር የተያያዘ ቀጭን መስመር መኖሩን እናያለን። መንግሥትም ቢኾን በቀጥታ አይገባም፤ ነገር ግን ፍርሃት እንደ ሥርዓት ዘዋሪ (system driver) ይኾናል። እንደ ሚሸል ፉኮ አገላለጽ ኃይል ከተማከለ ሥርዓት የሚመነጭ ሳይኾን በየትኛውም ቦታና ጊዜ በፍርሃት፣ በልማድ፣ በንግግር … ሊከሰት የሚችል ሂደት አይደል?
መዝሙረ ሄላም ላይ ታሪክ እንደ “circulation of social energy” ቀርቧል። መዝሙረ ሄላም ላይ መረጃ ከመንግሥት አይመጣም፤ ከግለሰብ እንጂ። የከተማ መሬት ዐዋጅም ኾነ የተማሪዎች ዘመቻ በገጸባሕርያቱ ወሬ ውስጥ ነው የሚንቀረቀበው። ይህ የመረጃ ሥርዓት ኃይል ማን እንዳለው ማን እንደሌለው ያሳያል። እንግዲህ ይህ በፉኮኛ micro-power መኾኑ ነው። በመዝሙረ ሄላም ላይ ታሪክ እንደ ወሬ እንጂ እንደ ሰነድ አይቀርብም።
ወሬ የፍርሃት ቤንዚን ነው … ፍርሃት ደግሞ በዝምታ መሸበብን ይፈጥራል … የዝምታ አፈ-ሙቅ ደግሞ ኃይለኛው እንዳይታይ ያደርጋል … የተደራጀው ኃይል ጥፋትን ሊያደርስ ባሰበ ቁጥር የወሬ ቤንዚን ይጨምራል። ሰዎች በዕቅብተ-ንግግር ራሳቸውን ሲሸብቡ ደርዝ ያለው ሙግት ይኮሰምናል፣ ንግግር ሲጠፋ ያልታወቀ አደጋ ይከሰታል፣ ፍርሃትም ይጨምራል። ያልታወቀ አደጋ ደግሞ ከታወቀ አካል ይመጣል። ስለዚህ ጥንስሱ የሚጀምረው ከወሬ እንደኾነ ያስመለክተናል። አዳም በመዝሙረ ሄላም ላይ ታሪክን እንደ “circulation of social energy” ሲያቀርብ ፕሬዝዳንት፣ ጀነራል፣ ፕሮፌሰር የኾኑ ታሪክ ከላዕላይ ያስቀመጣቸው ሰዎች አያስፈልጉትም። በአንጻሩ ሄላም ለማን እንደሳመችው ተደርጎ ብርሃኔ ያስወራው ወሬ፣ የሄላም አባት ወታደር በመኾኑ ምክንያት በካሱ፣ በሄኖክ እናት የተነዛው ወሬ እና ሄላም ከሄኖክ ጋር የተቆራረጠችበት መንገድ እንዲሁም የሄላምን የጡት ወተት በተመለከተ የተነዛው ወሬን ይጠቀማል።
መዝሙረ ሄላምን ከድኅረ-ቅኝ-አገዛዝ የኂስ መንገድ አንጻር እንመልከተው።
እውን ቅኝ-ግዛት ተረት ኾኖ ቀርቷል? በፖለቲካ፣ በኢኮኖሚ፣ በሥነልቦና ረገድ የቅኝ አገዛዝ ዳናው ሙሉ ለሙሉ ጠፍቷል? አዳም በመዝሙረ ሄላም ጽሑፍ ውስጥ ከቅኝ-ግዛት በተወረሰ መዋቅር ምክንያት የተሰናከለን ሕይወት ሊያስመለክተን ይኾን?
“ከተሞች ከቅኝ ግዛት በኋላ ሁለት ዓይነት መልክ ይኖራቸዋል፤ ለጥቂቱ የተድላ፣ ለተቀረው ደግሞ የአሳር መንደር ይኾናሉ” ይላል ፍራንዝ ፋኖን። በመዝሙረ ሄላም ላይ እና “የቢሾፍቱ ልጆች ጥላሞት” የተሰኘው ድርሰት ላይም ይህንን ነው የምንመለከተው። “ይወስዳል መንገድ ያመጣል መንገድ …” በተሰኘው መጽሐፉ ውስጥ ካሉ ጽሑፎች መካከል “የቢሾፍቱ ልጆች ጥላ ሞት” አንዱ ነው። የቢሾፍቱ ልጆች ሆቴሉን ያዩታል፤ ግን አይገቡበትም። ሆቴሉ የሀገራቸው መሬት ላይ ነው፤ እነርሱ ግን ከሆቴሉ ውጭ ናቸው። መናፈሻው ውስጥ አንዲት የፈረንጅ ልጅ ጠግባ ለልጆቹ እንደ ውሻ ዳቦ ትወረውርላቸዋለች። አፈር ላይ የወደቀን ዳቦ አራግፈው ይመገባሉ። በገዛ ሐይቃቸው ዳር ላይ ናቸው፤ ሌሎች ግን በጀልባ እየተንሸራሸሩ ይንፈላሰሳሉ። ለፈረንጆቹ ያደረው ሞገስ የላንድሮቨር ተፈናጣጭ ኾኗል። ሌሎቹ ግን ከመኪናው ውጪ ናቸው። ሞገስ እንደ እነርሱ ሕጻን ቢኾንም ለፈረንጅ በማሸርገዱ የትምህርት ቤቱ ባለቤት ሲመስል ሌሎች ልጆች ግን በገዛ መምህራቸው ይብጠለጠላሉ። የቢሾፍቱ ልጆች፣ ነጻ በተባለች ሀገር እየኖሩ በቅኝ ግዛት ጥላ ይተዳደራሉ። የቢሾፍቱ ልጆች በገዛ መንደራቸው አካሉ በማይታይ የቅኝ ግዛት እጅ ይገፋሉ። ሞገስ አይናገርም፤ የሚናገርለት አለ። ልክ የቢሾፍቱ ልጆች ላይ በአንድ ከተማ ውስጥ ሁለት የከተማ ምሥል እንደምናገኘው ሁሉ “የስንብት ቀለማት” ላይም በአዲስ አበባ ውስጥ ሁለት የከተማ ምሥል እንመለከታለን። እንደ ዘድሬክ፣ ሳተርን፣ ከተስፋዬ ወደ አሸናፊ የተቀየሩ የድሎት ምሥሎች እና የእነምትክ ጉልት፣ የእትየ እልልታ የጉርሻ መሸጫ መስኮት ያሉ የእጦት ሥዕል እናገኛለን። መዝሙረ ሄላም ላይም እንዲህ ያለ በአንድ ከተማ ላይ የሁለት ምሥሎች አደባባይ እጀግ ብዙ ቦታ ይገኛል።
በሌላኛው የድኅረ-ቅኝ-ግዛት ኂስ (postcolonial criticism) መዝሙረ ሄላምን ስንመለከት መጀመሪያ ላይ “ፈረንጅ ሲያደንቀኝና ሲገረምብኝ የሰሙ የአገሬ ደነዞች በየተራ “ካላስ የኔ ጎሳ ናት” … እያሉ መሻማት ጀመሩ ትላለች - ሄላም። በኋላ ደግሞ በተነዛባት አጓጉል ወሬ … የሄላምን ጡት ንቀው፣ አንጓጥጠው፣ አባረዋት ሲያበቁ የፈረንጅ የዱቄት ወተትን ይመርጣሉ። ይህ በባሕላዊ ማንነትና በዘመናዊነት መካከል የሚዋልል ማኅበረሰብን ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ የድኅረ-ቅኝ-ግዛት አካል ነው። በሌሎቹ የአዳም ሥራዎች ውስጥ ድኅረ-ቅኝ-ግዛት አተያይ በቋንቋና በኪነ-ጥበብ ምርጫ ውስጥ እንዴት እንደሚንፀባረቅ ያሳያል። በመዝሙረ ሄላም ላይ ደግሞ ምዕራባዊው ዓለም ለአገር በቀል መፍትኼ-ሥራይ የሚሰጠው ዋጋ ዝቅተኛ መኾኑንና የኢኮኖሚ ብዝበዛው አሁንም በረቂቅ መንገድ መቀጠሉን ያሳያል። እዚህ ላይ ሥዕለማርያም የተባለችዋን ገጸባሕርይ እና በውጭ ሀገራት የተነዙ ወሬዎችን ስንጨማምር ደግሞ የበለጠ ብዙ ለማለት ያስችላል።
መዝሙረ ሄላም ላይ እጅግ ብዙ ማኅበረሰባዊ ኂስ እናገኛለን። ለአብነት ያህል አንድ ሁለቱን እንቃኝ።
“መዝሙረ ሄላም” ላይ ማኅበረሰቡ በችላ-ባይነት አልያም በኾን ተብሎነት ልጆቹን ምን ያህል ተጠቂ እንዳደረጋቸው የሚያሳይ መልክ ተንጸባርቆበታል ማለት ይቻላል። ጋሽ ክብካብና ዘመናይ ኾን ብለው ቴዲና ሄላም ላይ የሚያደርሱትን፣ ተክለማርያም የወላጁን(የዘሪቱን) ችላ-ባይነት ለአብነት ማቅረብ ይቻላል። ማኅበረሰቡ ልጆችን “የነገ ተስፋዎች” ይላል፤ ነገር ግን ዛሬያቸው ላይ አይሠራም።
ማኅበረሰብ የመማጸኛ ከተማዎችን ወደ ተጨማሪ ግፍ መሥሪያ ቦታዎች እንደሚቀይር በአዳም መጻሕፍት ላይ በብዛት እንመለከታለን። “ይወስዳል መንገድ …” ላይ … “ቀዳዳ” በተሰኘው ታሪክ ላይ ማርታ ለደበበ በምትሰጠው ፍቅር ሳቢያ የሚሠራበትን ግፍ የምታስረሳ ብትኾንም ማኅበረሰቡ ግን ተጨማሪ ግፍ የሚሠራበት መሣሪያ ኾናለች። የስንብት ቀለማት ላይ ምኒልክ ከዚያ ሁሉ እስርና እንግልት በኋላ፣ “በፊያሜታ አርፋለሁ” ብሎ ቤቷ ሲሄድ ተጨማሪ ሕመም በጆሮው በኩል ጭንቅላቱ ላይ ይሻጥበታል። መዝሙረ ሄላም ላይም፣ ሄላም “ሙዚቃዬን ከሕዝብ ጆሮ ያደርስልኛል … ያሳርፈኛል …” ብላ የተመካችበት ምናሴ እንጦሮጦስ ይጨምራታል። ማኅበረሰባችን የመስቀል ተ ሠላጢን ግብር እንዳለው፣ ከላይ አሳልሞ ከታች በአንካሴው ጉድጓድ እንደሚምስ ያሳያል። ይህም የመልእክትን ወጭት ሰብሮ የወጣ ጥበባዊ አጻጻፍ ነው። በፈጣጣው የቀረበ የትችት ኮሶ አይደለም። ድንቅ ነው!
መዝሙረ ሄላም ላይ ከምናገኛቸው ዋና ዋና ገጸባሕርያት የተወሰኑት (አሮን፣ ቃል፣ ምናሴ፣ ሄላም) ላይ መጠነኛ ቅኝት እናድርግ።
auto-fiction ዓይነት አጻጻፍ ባለው የአሮን አተራረክ ውስጥ አሮን “system observer” መኾኑን እንገነዘባለን። ሥርዓቱን ያያል፣ ዘማቹን ያስተውላል፣ ቃለጉባኤ ይይዛል፣ ችግሩን ይመለከታል፣ ይጽፋል። አሮን የተገፋ ታሪክ ድምፅ ነው፤ ንቃት አለው፣ ግን የታሪክ ሂደትን የሚቀይር ኃይል የለውም፤ ስለዚህም ያ ሁሉ የጻፈውን ጽሑፍን ያጣል። የንቃት ችግር የለበትም፤ የማኅበራዊ ንቃት ድምፅነቱን ከዘመነ አባት ጋር ባደረገው ውይይት ውስጥ ተመልክተናል። ግን ደግሞ ይህ ብቻውን የቆመ ነጠላ ነገር ነው፤ ምክንያቱም ማኅበራዊ ተሳትፎ የለበትም። ቃል የተሰኘችው ገጸባሕርይም እንደ አሮን ናት፤ ንቃት ያላት፣ system observer ናት። ማኅበራዊ ንቃት ማኅበራዊ እንቅስቃሴ ካላገዘው ግንጥል ጌጥ ነው። ቃልና አሮን ንቃት አላቸው፤ ግን ንቃታቸውን ተግባር አላገዘውም፤ ንቃቱን የሚተገብር አደረጃጀት የላቸውም። ስለዚህ ዕጣ-ፈንታቸው ውድቀት ይኾናል። በኢትዮጵያ ውስጥ የተንሰራፋውን ይህን የድግግሞሽ አዙሪት መዝሙረ ሄላም ላይ ደራሲ አዳም ረታ በሰላ ብዕር አስቀምጧል።
የደራሲና የአርታኢ ትስስር በተንጸባረቀበት በሄላም አተራረክ ውስጥ ምናሴ የተሰኘ ገጸባሕርይ እናገኛለን። ምናሴ የ-false collective consciousness ትእምርት ነው። ምናሴዎች ለሥልጣን ይሠራሉ፣ ራሳቸውን እንደ ነጻ ያስባሉ፤ ነገር ግን የሥርዓቱ የመጠቀሚያ መሣሪያ (system functionary) ናቸው። ምናሴዎች የኦልቪቴዎች ጥይት ናቸው። ምናሴዎች የሔላምዎች ስኬት ሳይኾን የገዛ ጥቅማቸውን የሚያስቀድሙ የማኅበረሰቡ አካል ናቸው። ምናሴ በሌላ መነጽር ብናየው የመንግሥት ቢሮክራት የመካከለኛው መደብ ውክል ነው። ሀገሩ ከንጉሣዊ ሥርዓት ወደ ወታደራዊ ሥርዓት ቢቀየርም፤ ከወታደራዊ ሥርዓት ወደ ሌላ ሥርዓት ቢለወጥም ምናሴያውያን ግን አይቀየሩም። ሥርዓት ይቀየራል - ምናሴያውያን አይቀየሩም፣ ትእዛዝ ይፈጽማሉ፣ ይከድራሉ። ይህ በኢትዮጵያ ፖለቲካል-ታሪክ ውስጥ የተደጋገመ፣ ግን ደግሞ ያልተስተዋለ እውነት ነው።
ሄላም የወታደር ልጅ ናት፤ እንዲያሳድጋት በአደራ የተሰጠው ቤተሰብ የሚበድላት። የሷ ዓይነት ዕጣ ከደረሰው እንደ ወንድሟ ከምታየው ቴዲ ከሚባል ልጅ ጋር ታድጋለች። መጀመሪያ የሚልዮን፣ የኋላ ኋላ የምናሴ ፍቅረኛ የምትኾን ድምፀ-መረዋ ሴት ናት። ሁሉ ነገሯን ባጣችበት ወቅት ጡቷ ተአምር ያመርታል።
በመዝሙረ ሄላም ላይ የሄላም የጡት ወተት የአንዳች ነገር ውክል ይመስለኛል። ሻዕቢያ ለታጋይ ወጣቶች ማሳደጊያ ፈልጓት ሊሰርቃት መፈለጉ በቀላሉ የሚዘለል ነገር ነው? ወተት እና ጡት በመጀመሪያ እይታ የሕፃናት ትዝታ፣ የእናትነት ምሥል፣ የእምነት እና የጾታ መነሳሳት የተዋሃዱበትም አይደል? ወተት ሕይወት ነው? የመጀመሪያ ምግብ፣ ከእናት ወደ ልጅ የሚፈስም አይደል? በክርስቲያናዊ ምልክት ንጹሕነትን አይወክልም? ወተት ከ“ቅዱስ” ወደ “ሥጋዊ” የሚያስተላልፍ ድልድይ ነው ማለት እንችል ይኾን? የሄላምን ጡት የጠባ ታማሚ ልጅ እንዴት ጤናማ ሊኾን ቻለ? የምን ትእምርት ነው? ሄላም ከብዙ ወንድ ጋር የወጣች እንደመኾኗ ለዚህ ሰናይ ግብር ለምን የሷ ጡት ተመረጠ?
ሌላው፣ መዝሙረ ሄላም ላይ ኦልቬቲን እናገኛታለን። ኦልቬቲ የግራጫ ቃጭልዋ። መዝገቡ ንፋስ መውጫ ሳለ፣ ባልንጀራው ኤልያስ የብልግና ሀሁ ሊያስተምረው እፊቱ ያቆማት ቀይ ሰሌዳ ነበረች ኦልቬቲ። መዝሙረ ሄላም ላይ ምናሴን እና ቤተሰቡን የምታሾር ዐውራ ገጸባሕርይ ኾና ትከሰታለች። መዝሙረ ሄላም እና ግራጫ ቃጭሎች በጋለሞታይቱ በኦልቬቲ ብቻ ሳይኾን በዘመነ እንድርያስ እና በመዝገቡ ዱባለም ይገናኛሉ። ነጋ ዳቦ ጋጋሪውም በ-typological space መዝሙረ ሄላም ላይ እናገኘዋለን።
መዝሙረ ሄላምን ከህላዌነት (Existentialism) አንጻር እንመልከተው። ሄላም ትርጉም በማይሰጥ ዓለም ውስጥ እንዴት እንደምትኖር እናነባለን። የሀገሯ ዳር ድንበር እንዳይነካ አባት ብታዋጣም አሳዳጊዎቿ ግን የወላጅን ፍቅር አዋጥተው አይለግሷትም። ወርቅ አበድራ ጠጠር ትነፈጋለች። ዕቃ ለማገዝ ቤቷ ድረስ ለመጣው ሚልዮን ልቧን ትሰጣለች። ሀና የሸነቆረችውን ክፍተት ለሞላችበት ውለታዋ ክፍያ ይኾን ዘንድ ሚልዮን ለሄላም የወለፈንዴ ቡጢ ያሳርፍባታል። ለሕይወት ትርጉም ለመስጠት ባስ ውስጥ ካገኘችው ሄኖክ ጋር ብትሞክርም የበለጠ የሕይወት ትርጉም ይዛባባታል። የወታደር ልጅ መኾኗ ሄላምነቷን በዜሮ ያባዘዋል። የመጨረሻው ስንብትም ከሄኖክ ጓደኛ አፎት በሚወጣ ሰይፍ መቀላት ይኾናል። ከሄኖክ ጓደኛ ጀርባ የሚውለበለበው ባንዲራ ደግሞ የሄኖክ ሸሚዝ መኾኑ ደግሞ ቁስሉን እንደ አቡሰዲቅ ያደርገዋል። ለሕይወቷ ትልቅ ትርጉም ያለውን የሙዚቃ ሥራዋን፣ “ትርጉም ወዳለው
ነገር ይቀይርልኛል” ብላ በምትተማመንበት በምናሴ ትነጠቃለች። ተአምር በሚያስብለው በጡት ወተት ምክንያት ለሕይወቷ ትርጉም ለመስጠት ትታትራለች። የጡት ወተቷን ምርምር በማድረግ ለትልቅ ዓለምአቀፍ በጎ ተፅዕኖ ታደርጋለች ተብላ የተቆጠረችው ሥዕለማርያም የዓለም አቀፍ መሳለቂያና ትችት ምንጭ ትኾንባታለች። ይህ ሁሉ ትርጉም የሌለው ድግግሞሽ ነው። ይህ ደግሞ በሳርተር የተገለጸውን “existence without essence”-ን ያሳያል።
የህላዌነት መሠረታዊ ሐሳብ ነጻነት ነው፤ ግን ነጻነት ፍርሃትን ይወልዳል። ሄላም ለአሮን ፍቅሯን መናገር ትችላለች፤ ነገር ግን ዝምታን መርጣለች። የግራጫው መዝገቡ፣ የእንጀራ እናቱ የምታደርስበትን በደል እንደሚያውቀው ሁሉ ሄላምም ክብካብና ዘበናይ የሚያደርሱባትን አድሎ ታውቃለች፤ ግን ለረዥም ጊዜ ዝም ብላለች። ሄላም፣ ሙዚቃዋን ካጣች በኋላ ወደ ባንዱ ሄዳ መጋፈጥ ትችላለች፤ ነገር ግን አትሄድም … ይህ በሳርተርኛ bad faith ነው።
የሄላም ምርጫ ዝምታ ኾነ እንጂ ደካማ ናት ማለት አይደለም። “አልተናገርኩም ማለት አላውቀውም ማለት አይደለም” የሚል ዝምታ ነው ያላት። በሌላ ጎኑ ደግሞ ዝምታዋ፣ የለመደችውን ግፍ ከማታውቀው ዐዲስ ግፍ የመምረጥ ኹኔታ ነው። ዐዳዲስ ግፎችን ለመሸሽ በዝምታ አላዋቂነት ዛጎል ውስጥ የመደበቅ ብቃት ነው። የለመደችውን ግፍ የመከላከል አቅም ስላላት ባለመደችው ግፍ እንዳያጠፏት ሠግታ በውስጣዊ ንቃተ ሕሊና የዘየደችው ብልሃት ሊኾን ይችላል። ዝምታዋ የመቆየቷ ምሥጢር ነው። ደበበ ቀዝቃዛ ገለልተኛ ነኝ የሚለው ሰው ለመኖር ሲል ሳይታወቀው ስሜቱን የሚቆጣጠርበት መንገድን ለማስታወስ ነው።
“የስንብት ቀለማት” ገጸባሕርይ የኾነው ዮሴፍም ብዙ ነገር ያውቃል፤ ግን ዝም ይላል … ፊያሜታ ቂል መስሏት ትዘባርቃለች … እሱ ግን “አልተናገርኩም ማለት አላውቀውም ማለት አይደለም” የሚል የዝምታ መልስ ይመልስላታል። እሷ ግን ዝምታው አይገባትም። የ“ቀዳዳ”ው ደበበ እና “የስንብት …” ዮሴፍ ቀዳዳውን አይሞሉትም፤ እያዩት ይኖራሉ። ዶነሮች ጥሩ ፈንድ ሲለቁ ፊያሜታ ፕሮጀክቱን ለአሳምነው ትሰጠውና ዮሴፍን “ምን ዶነሮች እኮ ጠፉ ትለዋለች” … ዝም ይላል፤ ይታዘባል።
ቃል መሣሪያ ነበር፤ በዘመነ ደበበ፣ በዘመነ ዮሴፍ፣ በዘመነ ሄላም እና በዘመነ መዝገቡ ዱባለ ግን ቃል አደገኛ ኾኗል፤ ዝምታ ኹነኛ መጠጊያ ነው … ይህ ከደርግ በኋላ የተፈጠረ “traumatized literary silence” ማሳያ ነው። ስለኾነም ተራኪዎቹ (ደበበ፣ መዝገቡ፣ ዮሴፍ እና ሄላም) ለምን ዝም አሉ ሳይኾን "ዝምታን የሚያመነጭ ሥርዓት ምን ይኾን?" ብለን እንድንጠይቅ ያደርጋል። ግለሰብ ዝም ሲል፤ ሕዝብ በጸጥታ ይዋጣል፤ የዚያኔ የተማከለው ኃይል አፍ ያወጣል።
የአዳምን ዐዲሱን መጽሐፍ "በንባብ ይለቅ" ብለን መርቀናል።
ቢኒያም አቡራ
ሐምሌ 25 / 2018 ዓ.ም
Sponsored by
Surafel
1 day ago
የጨጓራ ህመም ተገቢዉን ህክምና ካላገኘ የምግብ መተላለፊያ ቱቦን በመዝጋት ለከፋ የጤና ችግር ሊያጋልጥ ይችላል ተባለ
የጨጓራ ህመምን በቤት ዉስጥ በተለያዩ መንገዶች ማከም አንዱ አማራጭ ቢሆንም ደረጃዉ ከፍ ሳይል ተገቢዉን የህክምና አገልግሎት ካላገኘ ለከፋ የጤና ችግር እንደሚያጋልጥ ተገልጿል።የጨጓራ ህመም ተገቢዉን የህክምና እርዳታ ካላገኘ እና ወደ መጨረሻዉ ደረጃ ከፍ ካለ ቁስለቱ እስከ መድማት ደርሶ ደም ማስመለስን ሊያስከትል ይችላል ።
የጨጓራ ቁስለት በከፍተኛ ደረጃ ተባብሶ የጨጓራ ግድግዳን ሙሉ በሙሉ በመብሳት ቀዳዳ በሚፈጥርበት ወቅት በሆድ ዕቃ ውስጥ ከባድ ኢንፌክሽንን ስለሚያስከትል አስቸኳይ የሕክምና እርዳታ ማግኘት ተገቢ ነዉ ተብሏል ።በተጨማሪም ጨጓራ ከትንሹ አንጀት ጋር የሚገናኝበት ቦታ ላይ በተደጋጋሚ ጉዳት ሲደርስበት ቦታዉ ይጠብና የምግብ መተላለፊያ ቱቦን በመዝጋት ለከፋ የጤና ችግር ስለሚያጋልጥ ተገቢዉን የህክምና እገዛ ማድረግ አስፈላጊ እንደሆነ በየካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ የዉስጥ ደዌ ስፔሻሊስት ዶክተር አምደመስቀል መርሻ ከብስራት ሬዲዮ ጋር ባደረጉት ቆይታ ተናግረዋል ።
የህክምና ባለሙያው አክለዉም በአንዳንድ ሰዎች ላይ በጨጓራ ባክቴሪያ አማካኝነት ወደ ካንሰር የመቀየር ዕድል ሊኖረዉ እንደሚችል አስገንዝበዋል።ለህመም ማስታገሻ ተብለዉ የሚወሰዱ እንደ አይቡፕሮፌን እና አስፕሪን ያሉ መድሃኒቶች ለረጅም ጊዜ የሚወሰዱ ከሆነ ለጨጓራ ቁስለት ሊያጋልጡ ይችላሉ በማለት የህክምና ባለሙያው ጨምረው ለብስራት ሬድዮ ተናግረዋል።
Seledadotio
Seledadotio
የጨጓራ ህመምን በቤት ዉስጥ በተለያዩ መንገዶች ማከም አንዱ አማራጭ ቢሆንም ደረጃዉ ከፍ ሳይል ተገቢዉን የህክምና አገልግሎት ካላገኘ ለከፋ የጤና ችግር እንደሚያጋልጥ ተገልጿል።የጨጓራ ህመም ተገቢዉን የህክምና እርዳታ ካላገኘ እና ወደ መጨረሻዉ ደረጃ ከፍ ካለ ቁስለቱ እስከ መድማት ደርሶ ደም ማስመለስን ሊያስከትል ይችላል ።
የጨጓራ ቁስለት በከፍተኛ ደረጃ ተባብሶ የጨጓራ ግድግዳን ሙሉ በሙሉ በመብሳት ቀዳዳ በሚፈጥርበት ወቅት በሆድ ዕቃ ውስጥ ከባድ ኢንፌክሽንን ስለሚያስከትል አስቸኳይ የሕክምና እርዳታ ማግኘት ተገቢ ነዉ ተብሏል ።በተጨማሪም ጨጓራ ከትንሹ አንጀት ጋር የሚገናኝበት ቦታ ላይ በተደጋጋሚ ጉዳት ሲደርስበት ቦታዉ ይጠብና የምግብ መተላለፊያ ቱቦን በመዝጋት ለከፋ የጤና ችግር ስለሚያጋልጥ ተገቢዉን የህክምና እገዛ ማድረግ አስፈላጊ እንደሆነ በየካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ የዉስጥ ደዌ ስፔሻሊስት ዶክተር አምደመስቀል መርሻ ከብስራት ሬዲዮ ጋር ባደረጉት ቆይታ ተናግረዋል ።
የህክምና ባለሙያው አክለዉም በአንዳንድ ሰዎች ላይ በጨጓራ ባክቴሪያ አማካኝነት ወደ ካንሰር የመቀየር ዕድል ሊኖረዉ እንደሚችል አስገንዝበዋል።ለህመም ማስታገሻ ተብለዉ የሚወሰዱ እንደ አይቡፕሮፌን እና አስፕሪን ያሉ መድሃኒቶች ለረጅም ጊዜ የሚወሰዱ ከሆነ ለጨጓራ ቁስለት ሊያጋልጡ ይችላሉ በማለት የህክምና ባለሙያው ጨምረው ለብስራት ሬድዮ ተናግረዋል።
Seledadotio
Seledadotio
1 day ago
#tecno_spark_50
አዲሱ የቴክኖ ስፓርክ 50 ቀኑን ሙሉ ሲሰሩበት ቢውሉ፣ ማህበራዊ ሚዲያ ቢጠቀሙበት፣ ስልክ ቢያወሩበት እንዲሁ ሌሎች ተያያዥ ነገሮችን ቢሰሩበት ከጠዋት እስከ ማታ ንቅንቅ አይልም ለምን? እጅግ ከፍተኛ የሆነ 6700 ሚሊ አምፒር ባትሪውን ይዞ ስለመጣ ነው፡፡ አዲሱ ቴክኖ ስፓርክ 50 ለስራዎት ያስፈልጎታል!!
#spark50 #spark50series #tecnoai #tecnoet
tecno_et
አዲሱ የቴክኖ ስፓርክ 50 ቀኑን ሙሉ ሲሰሩበት ቢውሉ፣ ማህበራዊ ሚዲያ ቢጠቀሙበት፣ ስልክ ቢያወሩበት እንዲሁ ሌሎች ተያያዥ ነገሮችን ቢሰሩበት ከጠዋት እስከ ማታ ንቅንቅ አይልም ለምን? እጅግ ከፍተኛ የሆነ 6700 ሚሊ አምፒር ባትሪውን ይዞ ስለመጣ ነው፡፡ አዲሱ ቴክኖ ስፓርክ 50 ለስራዎት ያስፈልጎታል!!
#spark50 #spark50series #tecnoai #tecnoet
tecno_et
1 day ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የሚኒሶታ ጤና መምሪያ በግዛቲቱ በሚገኙ የሜክሲኮ ምግብ ቤቶች ውስጥ ከሚቀርበው ሃላፒኖ የሚባለው የቃሪያ ዓይነት (የሜክሲኮ ቃሪያ) ጋር የተያያዘ የ'ሳልሞኔላ ጃቪያና' ወረርሽኝን እየመረመረ መሆኑን አስታወቀ። መምሪያው እስካሁን 110 የተረጋገጡ የሳልሞኔላ ታማሚዎች መመዝገባቸውን ገልጿል።
የጤና ባለስልጣናት ህመሙ ከተከሰተባቸው ሰዎች መካከል 84ቱን ያነጋገሩ ሲሆን፣ ከእነዚህ ውስጥ 75 በመቶ የሚሆኑት ከሰኔ 14 እስከ ሀምሌ 14 ባለው ጊዜ ውስጥ 'ቺፖትሌ' በተባለው ታዋቂ ምግብ ቤት የተመገቡ መሆናቸውን ጠቁመዋል። ቀሪዎቹ ደግሞ በሌሎች የሜክሲኮ ምግብ ቤቶች መመገባቸውን ተናግረዋል። ወረርሽኙን ተከትሎ ቺፖትሌ በሚኒሶታ ከሚገኙ በርካታ ቅርንጫፎቹ ሃላፔኖ ቃሪያዎችን ማንሳቱን አስታውቋል።
የቺፖትሌ ቃል አቀባይ በሰጡት መግለጫ፣ "ሊከሰት ስለሚችለው ወረርሽኝ እንደሰማን ወዲያውኑ የክትትል ስርዓታችንን በመጠቀም ሃላፔኖ ቃሪያው የተሰራጨባቸውን ምግብ ቤቶች ለይተናል፤ ለጥንቃቄ ሲባልም የተጠረጠሩትን ምርቶች ከምግብ ቤቶቻችን በማስወገድ ከሌሎች አምራቾች በተገኙ ቃሪያዎች ተክተናል" ብለዋል። በሚኒሶታ ጤና መምሪያ የምግብ ወለድ በሽታዎች ክፍል ከፍተኛ ኤፒዲሚዮሎጂስት ካርሎታ ሜዱስ በበኩላቸው፣ ቺፖትሌ ከምርመራው ጋር በተያያዘ መረጃዎችን ከመስጠት ጀምሮ የተጠረጠሩትን ቃሪያዎች ለማስወገድ የወሰደውን ፈጣን እርምጃ በማንሳት የተቋሙን ሙሉ ትብብር አድንቀዋል።
የጤና መምሪያው ወረርሽኙ አሁንም እንደቀጠለ ለማወቅ ጊዜው ገና መሆኑን ቢገልጽም፣ ቺፖትሌ በወሰደው ፈጣን እርምጃ ምክንያት በድርጅቱ ላይ ስጋት እንደሌለው አስታውቋል። ሆኖም የተበከለው ቃሪያ በሌሎች ምግብ ቤቶች አሁንም እየቀረበ ከሆነ ወረርሽኙ ሊቀጥል እንደሚችል እና በቀጣይ ቀናት ተጨማሪ ታማሚዎች ሊመዘገቡ እንደሚችሉ ስጋቱን አጋርቷል።
ወረርሽኙን በፍጥነት ለመቆጣጠር የታማሚዎች መረጃ እጅግ ወሳኝ መሆኑን የገለጹት ካርሎታ ሜዱስ፣ የጤና ባለሙያዎች ምርመራቸውን የሚያካሂዱት ጥቆማ በደረሳቸው ታማሚዎች ላይ በመደወል በመሆኑ፣ ህብረተሰቡ ለሚደረጉ የስልክ ጥሪዎች ምላሽ በመስጠት ትብብር እንዲያደርግ ጥሪያቸውን አቅርበዋል።
የጤና ባለስልጣናት ህመሙ ከተከሰተባቸው ሰዎች መካከል 84ቱን ያነጋገሩ ሲሆን፣ ከእነዚህ ውስጥ 75 በመቶ የሚሆኑት ከሰኔ 14 እስከ ሀምሌ 14 ባለው ጊዜ ውስጥ 'ቺፖትሌ' በተባለው ታዋቂ ምግብ ቤት የተመገቡ መሆናቸውን ጠቁመዋል። ቀሪዎቹ ደግሞ በሌሎች የሜክሲኮ ምግብ ቤቶች መመገባቸውን ተናግረዋል። ወረርሽኙን ተከትሎ ቺፖትሌ በሚኒሶታ ከሚገኙ በርካታ ቅርንጫፎቹ ሃላፔኖ ቃሪያዎችን ማንሳቱን አስታውቋል።
የቺፖትሌ ቃል አቀባይ በሰጡት መግለጫ፣ "ሊከሰት ስለሚችለው ወረርሽኝ እንደሰማን ወዲያውኑ የክትትል ስርዓታችንን በመጠቀም ሃላፔኖ ቃሪያው የተሰራጨባቸውን ምግብ ቤቶች ለይተናል፤ ለጥንቃቄ ሲባልም የተጠረጠሩትን ምርቶች ከምግብ ቤቶቻችን በማስወገድ ከሌሎች አምራቾች በተገኙ ቃሪያዎች ተክተናል" ብለዋል። በሚኒሶታ ጤና መምሪያ የምግብ ወለድ በሽታዎች ክፍል ከፍተኛ ኤፒዲሚዮሎጂስት ካርሎታ ሜዱስ በበኩላቸው፣ ቺፖትሌ ከምርመራው ጋር በተያያዘ መረጃዎችን ከመስጠት ጀምሮ የተጠረጠሩትን ቃሪያዎች ለማስወገድ የወሰደውን ፈጣን እርምጃ በማንሳት የተቋሙን ሙሉ ትብብር አድንቀዋል።
የጤና መምሪያው ወረርሽኙ አሁንም እንደቀጠለ ለማወቅ ጊዜው ገና መሆኑን ቢገልጽም፣ ቺፖትሌ በወሰደው ፈጣን እርምጃ ምክንያት በድርጅቱ ላይ ስጋት እንደሌለው አስታውቋል። ሆኖም የተበከለው ቃሪያ በሌሎች ምግብ ቤቶች አሁንም እየቀረበ ከሆነ ወረርሽኙ ሊቀጥል እንደሚችል እና በቀጣይ ቀናት ተጨማሪ ታማሚዎች ሊመዘገቡ እንደሚችሉ ስጋቱን አጋርቷል።
ወረርሽኙን በፍጥነት ለመቆጣጠር የታማሚዎች መረጃ እጅግ ወሳኝ መሆኑን የገለጹት ካርሎታ ሜዱስ፣ የጤና ባለሙያዎች ምርመራቸውን የሚያካሂዱት ጥቆማ በደረሳቸው ታማሚዎች ላይ በመደወል በመሆኑ፣ ህብረተሰቡ ለሚደረጉ የስልክ ጥሪዎች ምላሽ በመስጠት ትብብር እንዲያደርግ ጥሪያቸውን አቅርበዋል።
1 day ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የቀድሞው የዓለም ባንክ ፕሬዝዳንት ዴቪድ ማልፓስን ሀሳብ ዋቢ በማድረግ ክቡር ገና ባወጡት ትንታኔ፣ በኢትዮጵያ እየተተገበረ ያለው የኢኮኖሚ ማሻሻያ እና የገንዘብ ፖሊሲ በተራው ዜጋ ላይ እያስከተለ ያለውን ጫና በጽኑ ተችተዋል። የኢኮኖሚ ቃላቶች እንደ "ማረጋጋት"፣ "ሊበራላይዜሽን"፣ "የገበያ መተማመን" እና "ተለዋዋጭ የምንዛሬ ተመን" የመሳሰሉት ዘመናዊነትን እና ኃላፊነትን የሚያንፀባርቁ ቢመስሉም፣ ከዚህ መረጋጋት ተጠቃሚው ማነው የሚለው ጥያቄ ግን ክሪቲካል መሆኑን ጽሁፉ ያነሳል።
የኢትዮጵያ መንግስት የብርን የምንዛሬ ተመን በገበያ እንዲወሰን ማድረጉ የማይቀር አማራጭ እንደነበር ይከራከራል። ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ተቋማትም ይህንን በመደገፍ የውጭ ምንዛሪ ገበያው በነፃነት እየሰራ መምጣቱን፣ የወጪ ንግድ ገቢ መጨመሩን፣ የዋጋ ግሽበት ከነበረበት ከፍተኛ ደረጃ መጠነኛ መሻሻል ማሳየቱን፣ እንዲሁም የዕዳ ሽግሽግ ሂደቱ እርምጃ እያሳየ መሆኑን እንደ አበረታች ውጤቶች ይጠቅሳሉ። ይሁን እንጂ፣ እነዚህ ማሻሻያዎች የዜጎችን ድህነት እንዳባባሱ እና የተራውን ኢትዮጵያዊ የመግዛት አቅም በከፍተኛ ሁኔታ እንዳዳከሙ የቀድሞው የዓለም ባንክ ፕሬዝዳንት ሞግተዋል። ክቡር ገና በጽሁፋቸው እንዳስገነዘቡት፣ እነዚህ ሁለት ተቃራኒ የሚመስሉ ሀሳቦች ስኬትን ከሚለኩበት መነፅር አንፃር የሚለያዩ እንጂ የሚጣረሱ አይደሉም። አንደኛው የማክሮ ኢኮኖሚ ተቋማትን ጤንነት ሲለካ፣ ሌላኛው ደግሞ የህብረተሰቡን ተጨባጭ የኑሮ ሁኔታ ይለካል።
አንድ ሀገር ያደገች የምትባለው የምንዛሬ ተመኗ በነፃ ገበያ ስለተመራ፣ የባለሀብቶች መተማመን ስለጨመረ ወይም የዕዳ ሽግሽግ ስለተደረገ አይደለም። እነዚህ ግቡን መምቻ መንገዶች እንጂ እራሳቸውን የቻሉ ግቦች አይደሉም። የጽሁፉ አቅራቢ እንዳስቀመጡት የእውነተኛ እድገት መለኪያዎች የምርት አቅም መስፋፋትን፣ የሰራተኞች ምርታማነት ማደግን፣ የኢንዱስትሪዎች አቅም መጎልበትን፣ የአርሶ አደሩ ምርት መጨመርን፣ ወጣቶች ትርጉም ያለው የስራ ዕድል ማግኘታቸውን፣ እንዲሁም ሀገሪቱ በውጭ ፋይናንስ ላይ ያላት ጥገኝነት መቀነሱን ያካትታሉ። ታሪክ እንደሚያስተምረው፣ የበለጸጉ ሀገራት መጀመሪያ ገበያቸውን በማስተካከል ሳይሆን፤ ምርታቸውን በማሳደግ፣ ስትራቴጂካዊ ኢንዱስትሪዎቻቸውን በመጠበቅ እና የቴክኖሎጂ አቅማቸውን በመገንባት ነው ሀብታም የሆኑት። ኢትዮጵያ ግን አሁን ላይ የፋይናንስ ማሻሻያውን በማስቀደም፣ መዋቅራዊ ሽግግሩን ወደ ኋላ በመተው የተገላቢጦሽ መንገድ እየተጓዘች መሆኗን ጽሁፉ ይተቻል።
የእነዚህን የኢኮኖሚ ማሻሻያዎች ጫና የሚሸከሙት ዓለም አቀፍ አበዳሪዎች፣ የፋይናንስ ተቋማት ወይም ሀብታቸው ዋጋ በሚጨምር ንብረቶች የተጠበቀላቸው አካላት አይደሉም። ይልቁንም የኢኮኖሚው ማሻሻያ ጫና በዋናነት የሚያርፈው በደመወዝ ተከፋዮች፣ በአነስተኛ የንግድ ተቋማት፣ በሸማቾች፣ ከውጭ የሚገቡ ግብዓቶችን ውድ በሆነ ዋጋ በሚገዙ አርሶ አደሮች፣ እና እጅግ ውድ ወደሆነው የስራ ገበያ አዲስ በሚቀላቀሉ ወጣቶች ላይ ነው። በመሆኑም እነዚህ የኢኮኖሚ ድንጋጤን የመቋቋም አቅም የሌላቸው የህብረተሰብ ክፍሎች፣ ለማክሮ ኢኮኖሚው መረጋጋት ዋነኛ ፋይናንስ አድራጊዎች ሆነዋል። ምንም እንኳን ይህ ጫና ጊዜያዊ መስዋዕትነት ተብሎ ቢቀርብም፣ ጊዜያዊ መስዋዕትነቶች ወደ ቋሚነት የመቀየር አዝማሚያ እንዳላቸው ታሪክ ያሳያል።
እርግጥ ነው የትኛውም ሀገር ስር በሰደደ የዋጋ ግሽበት፣ በተዛባ የምንዛሬ ተመን እና ሊቋቋመው በማይችለው የህዝብ ፋይናንስ ውስጥ ሆኖ ሊበለጽግ አይችልም። ነገር ግን ኢኮኖሚያዊ መረጋጋቱ የማንን ፍላጎት ለማሟላት ነው? መረጋጋቱ በራሱ ብቸኛ ግብ ከሆነ፣ ኢኮኖሚው ከልማት ቅድሚያዎች ይልቅ የፋይናንስ አመልካቾችን ወደ ማሟላት ይሸጋገራል። በውጤቱም፣ በጀቶች ጤናማ ሲሆኑ ቤተሰቦች እየደኸዩ ይሄዳሉ፤ የውጭ መተማመን ሲጨምር የሀገር ውስጥ የመግዛት አቅም ይዳከማል፤ በመጨረሻም የኢኮኖሚ ፖሊሲው ህዝብን ከማገልገል ይልቅ ገበያን እና አበዳሪዎችን ወደ ማርካት ይዞራል። የቀድሞው የዓለም ባንክ ፕሬዝዳንት ለማስታወስ እንደሞከሩት፤ የማክሮ ኢኮኖሚ ስኬት ማለት፣ ማህበራዊ ስኬት ማለት አይደለም። ታሪክ በመጨረሻ የሚጠይቀው ጥያቄ፣ ገበያው ቀልጣፋ መሆኑን፣ የምንዛሬ ተመኑ ተለዋዋጭ መሆኑን ወይም የዋጋ ግሽበቱ የታሰበው ግብ ላይ መድረሱን ሳይሆን ማሻሻያው ሀገሪቱን ከበፊቱ የበለጠ ጠንካራ አድርጓታል ወይ የሚለውን ነው። የማክሮ ኢኮኖሚ አመልካቾች እየተሻሻሉ ህዝቡ እየደኸየ የሚሄድባት ሀገር መረጋጋትን ልታመጣ ትችል ይሆናል፤ ነገር ግን እድገትን አምጥታለች ወይ የሚለው አሁንም ምላሽ ያላገኘ ትልቅ ጥያቄ መሆኑን ጽሁፉ በፅኑ ያስገነዝባል።
የኢትዮጵያ መንግስት የብርን የምንዛሬ ተመን በገበያ እንዲወሰን ማድረጉ የማይቀር አማራጭ እንደነበር ይከራከራል። ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ተቋማትም ይህንን በመደገፍ የውጭ ምንዛሪ ገበያው በነፃነት እየሰራ መምጣቱን፣ የወጪ ንግድ ገቢ መጨመሩን፣ የዋጋ ግሽበት ከነበረበት ከፍተኛ ደረጃ መጠነኛ መሻሻል ማሳየቱን፣ እንዲሁም የዕዳ ሽግሽግ ሂደቱ እርምጃ እያሳየ መሆኑን እንደ አበረታች ውጤቶች ይጠቅሳሉ። ይሁን እንጂ፣ እነዚህ ማሻሻያዎች የዜጎችን ድህነት እንዳባባሱ እና የተራውን ኢትዮጵያዊ የመግዛት አቅም በከፍተኛ ሁኔታ እንዳዳከሙ የቀድሞው የዓለም ባንክ ፕሬዝዳንት ሞግተዋል። ክቡር ገና በጽሁፋቸው እንዳስገነዘቡት፣ እነዚህ ሁለት ተቃራኒ የሚመስሉ ሀሳቦች ስኬትን ከሚለኩበት መነፅር አንፃር የሚለያዩ እንጂ የሚጣረሱ አይደሉም። አንደኛው የማክሮ ኢኮኖሚ ተቋማትን ጤንነት ሲለካ፣ ሌላኛው ደግሞ የህብረተሰቡን ተጨባጭ የኑሮ ሁኔታ ይለካል።
አንድ ሀገር ያደገች የምትባለው የምንዛሬ ተመኗ በነፃ ገበያ ስለተመራ፣ የባለሀብቶች መተማመን ስለጨመረ ወይም የዕዳ ሽግሽግ ስለተደረገ አይደለም። እነዚህ ግቡን መምቻ መንገዶች እንጂ እራሳቸውን የቻሉ ግቦች አይደሉም። የጽሁፉ አቅራቢ እንዳስቀመጡት የእውነተኛ እድገት መለኪያዎች የምርት አቅም መስፋፋትን፣ የሰራተኞች ምርታማነት ማደግን፣ የኢንዱስትሪዎች አቅም መጎልበትን፣ የአርሶ አደሩ ምርት መጨመርን፣ ወጣቶች ትርጉም ያለው የስራ ዕድል ማግኘታቸውን፣ እንዲሁም ሀገሪቱ በውጭ ፋይናንስ ላይ ያላት ጥገኝነት መቀነሱን ያካትታሉ። ታሪክ እንደሚያስተምረው፣ የበለጸጉ ሀገራት መጀመሪያ ገበያቸውን በማስተካከል ሳይሆን፤ ምርታቸውን በማሳደግ፣ ስትራቴጂካዊ ኢንዱስትሪዎቻቸውን በመጠበቅ እና የቴክኖሎጂ አቅማቸውን በመገንባት ነው ሀብታም የሆኑት። ኢትዮጵያ ግን አሁን ላይ የፋይናንስ ማሻሻያውን በማስቀደም፣ መዋቅራዊ ሽግግሩን ወደ ኋላ በመተው የተገላቢጦሽ መንገድ እየተጓዘች መሆኗን ጽሁፉ ይተቻል።
የእነዚህን የኢኮኖሚ ማሻሻያዎች ጫና የሚሸከሙት ዓለም አቀፍ አበዳሪዎች፣ የፋይናንስ ተቋማት ወይም ሀብታቸው ዋጋ በሚጨምር ንብረቶች የተጠበቀላቸው አካላት አይደሉም። ይልቁንም የኢኮኖሚው ማሻሻያ ጫና በዋናነት የሚያርፈው በደመወዝ ተከፋዮች፣ በአነስተኛ የንግድ ተቋማት፣ በሸማቾች፣ ከውጭ የሚገቡ ግብዓቶችን ውድ በሆነ ዋጋ በሚገዙ አርሶ አደሮች፣ እና እጅግ ውድ ወደሆነው የስራ ገበያ አዲስ በሚቀላቀሉ ወጣቶች ላይ ነው። በመሆኑም እነዚህ የኢኮኖሚ ድንጋጤን የመቋቋም አቅም የሌላቸው የህብረተሰብ ክፍሎች፣ ለማክሮ ኢኮኖሚው መረጋጋት ዋነኛ ፋይናንስ አድራጊዎች ሆነዋል። ምንም እንኳን ይህ ጫና ጊዜያዊ መስዋዕትነት ተብሎ ቢቀርብም፣ ጊዜያዊ መስዋዕትነቶች ወደ ቋሚነት የመቀየር አዝማሚያ እንዳላቸው ታሪክ ያሳያል።
እርግጥ ነው የትኛውም ሀገር ስር በሰደደ የዋጋ ግሽበት፣ በተዛባ የምንዛሬ ተመን እና ሊቋቋመው በማይችለው የህዝብ ፋይናንስ ውስጥ ሆኖ ሊበለጽግ አይችልም። ነገር ግን ኢኮኖሚያዊ መረጋጋቱ የማንን ፍላጎት ለማሟላት ነው? መረጋጋቱ በራሱ ብቸኛ ግብ ከሆነ፣ ኢኮኖሚው ከልማት ቅድሚያዎች ይልቅ የፋይናንስ አመልካቾችን ወደ ማሟላት ይሸጋገራል። በውጤቱም፣ በጀቶች ጤናማ ሲሆኑ ቤተሰቦች እየደኸዩ ይሄዳሉ፤ የውጭ መተማመን ሲጨምር የሀገር ውስጥ የመግዛት አቅም ይዳከማል፤ በመጨረሻም የኢኮኖሚ ፖሊሲው ህዝብን ከማገልገል ይልቅ ገበያን እና አበዳሪዎችን ወደ ማርካት ይዞራል። የቀድሞው የዓለም ባንክ ፕሬዝዳንት ለማስታወስ እንደሞከሩት፤ የማክሮ ኢኮኖሚ ስኬት ማለት፣ ማህበራዊ ስኬት ማለት አይደለም። ታሪክ በመጨረሻ የሚጠይቀው ጥያቄ፣ ገበያው ቀልጣፋ መሆኑን፣ የምንዛሬ ተመኑ ተለዋዋጭ መሆኑን ወይም የዋጋ ግሽበቱ የታሰበው ግብ ላይ መድረሱን ሳይሆን ማሻሻያው ሀገሪቱን ከበፊቱ የበለጠ ጠንካራ አድርጓታል ወይ የሚለውን ነው። የማክሮ ኢኮኖሚ አመልካቾች እየተሻሻሉ ህዝቡ እየደኸየ የሚሄድባት ሀገር መረጋጋትን ልታመጣ ትችል ይሆናል፤ ነገር ግን እድገትን አምጥታለች ወይ የሚለው አሁንም ምላሽ ያላገኘ ትልቅ ጥያቄ መሆኑን ጽሁፉ በፅኑ ያስገነዝባል።
1 day ago
ፍልሰታ በበአታ
“ትግሁ ወጸልዩ ከመ ኢትባኡ ውስተ መንሱት፤
ወደፈተና እንዳትገቡ ትጉና ጸልዩ “ማቴ 26፡40
የበአታ ገዳም መልዕክት
ይህን ታላቅ ጾም በታላቋ ገዳም በዳግማዊ ምኒልክ መታሰቢያ ታዕካነገሥት በአታ ለማርያም በደብረመንክራት
ሥዕልቤት ኪዳነምህረት ገዳም ፡፡
ይህ ጾመ ማርያም (ጾመ ፍልሰታ) ከ7ቱ ታላላቅ አጽዋማት አንዱ እንደሆነ ይታወቃል ይህን ጾም ከሌላው
ለየት የሚያደርገው አባቶቻችን ሐዋርያት ለትምህርተ ወንጌል ከተሰማሩበት ተሰባስበው የእመቤታችንን
ትንሳኤዋንና ዕርገቷን ለማየት ሁለት ሱባኤ ወይም ለ14ቀን ፈጣሪያቸውን በጸሎትና በምህላ ጠይቀው
ትንሳኤዋን እና ዕርገቷን ለማየት በቅተዋል፡፡እኛም የእነሱን መንገድ ተከትለን በቤተ እግዚአብሔር በጸሎት
በቅዳሴ በሰዓታት በምህላ ለሁለት ሱባኤ ወይም ለ14ቀን በየዓመቱ ሱባኤ ይዘን እንጸልያለን፡፡ ይህ ጾመ ሱባኤ
በታዕካ ነገሥት በአታ ለማርያም በስዕል ቤት ኪዳነምህረት ገዳም በልዩ ሁኔታ ይከናወናል፡፡ ሆኖም አሁን
ባለው ሁኔታ በገዳማችን አካባቢ የሚገኙ ምእመናን በመልሶ ማልማት ምክንያት ከስፍራው ርቀው ይገኛሉ ፡፡
ስለሆነም ይህ የጥሪ መልእክት የደረሳችሁ ምእመናን እና ምእመናት በሙሉ በገዳማችን መጥታችሁ ይህን
ታላቅ የሱባኤ ጾም እንድታከናውኑ እናሳስባለን፡
በሱባኤ ጊዜ በገዳማችን የሚከናወኑ መንፈሳዊ የሱባኤ አገልግሎቶች
1ኛ. ከምሽቱ 4ሰዓት እስከ ጠዋት 12፡30 የሰዓታት ቁመት ኪዳንን ጨምሮ ይከናወናል፡፡
2ኛ የውዳሴ ማርያም እና የቅዳሴ ማርያም ትርጉም ከ3፡30 እስከ 6፡00ሰዓት የካሄዳል፡፡
3ኛ ከ6፡00 ሰዓት እስከ 9፡00 ሰዓት የቅዳሴ አገልግሎት በሁለቱም ቤተ ክርስቲያን ይካሄዳል፡፡
4ኛ በገዳማችን ብቻ በተለየ መልኩ የሚጸለይ የሠርክ ጸሎት (የምህላ) አገልግሎት መሐረነአብ ተብሎ
እግዚኦ መሐረነክርስቶስ መቶ ጊዜ በእንተማርያም መሐረነክርስቶስ መቶ ጊዜ እየተባለ ከ9፡30 እስከ 11፡00
ሰዓት ይደረሳል ፡፡
5ኛ ከ11፡00 እስከ 12፡30 የትምህርተ ወንጌል መርሀ ግብር ይፈፀማል፡፡
ይህንን ጾመሱባኤ በእመቤታችን በበአታማርያም ደጅ መጥታችሁ በታላላቅአበው መነኮሳት እጅ
እየተባረካችሁ በመጨረሻም ነሐሴ16 ቀን በዚሁ ገዳም የኪዳነምህረት በአለንግሧን አንግሣችሁ በረከት
እንድታገኙ ጥሪያችንን በእግዚአብሔርስም እያስተላለፍን በበአታ ገዳማችን ተገኝታችሁ እንድትጸልዩ
ተጋብዛችኋል ፡፡
ረድኤተ እግዚአብሔር አይለየን አሜን።
“ትግሁ ወጸልዩ ከመ ኢትባኡ ውስተ መንሱት፤
ወደፈተና እንዳትገቡ ትጉና ጸልዩ “ማቴ 26፡40
የበአታ ገዳም መልዕክት
ይህን ታላቅ ጾም በታላቋ ገዳም በዳግማዊ ምኒልክ መታሰቢያ ታዕካነገሥት በአታ ለማርያም በደብረመንክራት
ሥዕልቤት ኪዳነምህረት ገዳም ፡፡
ይህ ጾመ ማርያም (ጾመ ፍልሰታ) ከ7ቱ ታላላቅ አጽዋማት አንዱ እንደሆነ ይታወቃል ይህን ጾም ከሌላው
ለየት የሚያደርገው አባቶቻችን ሐዋርያት ለትምህርተ ወንጌል ከተሰማሩበት ተሰባስበው የእመቤታችንን
ትንሳኤዋንና ዕርገቷን ለማየት ሁለት ሱባኤ ወይም ለ14ቀን ፈጣሪያቸውን በጸሎትና በምህላ ጠይቀው
ትንሳኤዋን እና ዕርገቷን ለማየት በቅተዋል፡፡እኛም የእነሱን መንገድ ተከትለን በቤተ እግዚአብሔር በጸሎት
በቅዳሴ በሰዓታት በምህላ ለሁለት ሱባኤ ወይም ለ14ቀን በየዓመቱ ሱባኤ ይዘን እንጸልያለን፡፡ ይህ ጾመ ሱባኤ
በታዕካ ነገሥት በአታ ለማርያም በስዕል ቤት ኪዳነምህረት ገዳም በልዩ ሁኔታ ይከናወናል፡፡ ሆኖም አሁን
ባለው ሁኔታ በገዳማችን አካባቢ የሚገኙ ምእመናን በመልሶ ማልማት ምክንያት ከስፍራው ርቀው ይገኛሉ ፡፡
ስለሆነም ይህ የጥሪ መልእክት የደረሳችሁ ምእመናን እና ምእመናት በሙሉ በገዳማችን መጥታችሁ ይህን
ታላቅ የሱባኤ ጾም እንድታከናውኑ እናሳስባለን፡
በሱባኤ ጊዜ በገዳማችን የሚከናወኑ መንፈሳዊ የሱባኤ አገልግሎቶች
1ኛ. ከምሽቱ 4ሰዓት እስከ ጠዋት 12፡30 የሰዓታት ቁመት ኪዳንን ጨምሮ ይከናወናል፡፡
2ኛ የውዳሴ ማርያም እና የቅዳሴ ማርያም ትርጉም ከ3፡30 እስከ 6፡00ሰዓት የካሄዳል፡፡
3ኛ ከ6፡00 ሰዓት እስከ 9፡00 ሰዓት የቅዳሴ አገልግሎት በሁለቱም ቤተ ክርስቲያን ይካሄዳል፡፡
4ኛ በገዳማችን ብቻ በተለየ መልኩ የሚጸለይ የሠርክ ጸሎት (የምህላ) አገልግሎት መሐረነአብ ተብሎ
እግዚኦ መሐረነክርስቶስ መቶ ጊዜ በእንተማርያም መሐረነክርስቶስ መቶ ጊዜ እየተባለ ከ9፡30 እስከ 11፡00
ሰዓት ይደረሳል ፡፡
5ኛ ከ11፡00 እስከ 12፡30 የትምህርተ ወንጌል መርሀ ግብር ይፈፀማል፡፡
ይህንን ጾመሱባኤ በእመቤታችን በበአታማርያም ደጅ መጥታችሁ በታላላቅአበው መነኮሳት እጅ
እየተባረካችሁ በመጨረሻም ነሐሴ16 ቀን በዚሁ ገዳም የኪዳነምህረት በአለንግሧን አንግሣችሁ በረከት
እንድታገኙ ጥሪያችንን በእግዚአብሔርስም እያስተላለፍን በበአታ ገዳማችን ተገኝታችሁ እንድትጸልዩ
ተጋብዛችኋል ፡፡
ረድኤተ እግዚአብሔር አይለየን አሜን።
1 day ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንጃሚን ኔታንያሁ የሀማስን ትጥቅ ለማስፈታት በቀረበው እና ሀማስ ባለፈው ሳምንት በተቀበለው የ"ቦርድ ኦፍ ፒስ" (የሰላም ቦርድ) እቅድ ላይ እስራኤል እንዳልተስማማች ለመጀመሪያ ጊዜ በይፋ ተናግረዋል። ኔታንያሁ ማክሰኞ ዕለት በፌስቡክ ገፃቸው ባወጡት የቪዲዮ መልእክት፣ ሀማስ ሙሉ በሙሉ ትጥቁን እስኪፈታ ድረስ እስራኤል አሁን በጋዛ ከያዘችው ይዞታ ወደ ኋላ እንደማታፈገፍግ በፅኑ አረጋግጠዋል።
ይህ የኔታንያሁ አቋም እስራኤል በጋዛ ወደነበረው የመጀመሪያው "ቢጫ መስመር" እንድትመለስ ከሚጠይቀው የአሜሪካ ድጋፍ ካለው የትጥቅ ማስፈታት እቅድ ጋር የሚቃረን ነው። እስራኤል በጥቅምት 2025 ከሀማስ ጋር በተደረገው የተኩስ አቁም እና ታጋቾችን የመልቀቅ ስምምነት መሰረት ወደዚህ መስመር አፈግፍጋ የነበረ ቢሆንም፣ ከዚያን ጊዜ ወዲህ ግን በሰርጡ ላይ ያላትን የቁጥጥር ድርሻ ከ53 በመቶ ወደ 60 በመቶ አሳድጋለች። የሰላም ቦርዱ ሀማስ መሳሪያውን ማስረከብ እስኪጀምር ድረስ እስራኤል ከቢጫው መስመር በላይ ማፈግፈግ እንደማይጠበቅባት ቢያመለክትም፣ ኔታንያሁ ግን የእስራኤል ጦር አሁን ካለበት ቦታ ንቅንቅ እንደማይል አስታውቀዋል።
ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ እና ቡድናቸው የሀማስን ትጥቅ ማስፈታት እንደሚችሉ በማሰብ ረቂቅ እቅድ እንደላኩላቸው የገለጹት ኔታንያሁ፣ እስራኤል ግን እቅዱን ሳትቀበል የራሷን ማስተካከያ መልሳ መላኳን አስረድተዋል። ይሁን እንጂ ይህ ረቂቅ በአሜሪካ፣ ግብፅ፣ ኳታር፣ ቱርክ እና ሀማስ መካከል በተደረገ የተናጠል ድርድር የተገኘ በመሆኑ ከእስራኤል ጋር ለድርድር ክፍት ይሆናል ተብሎ አልተጠበቀም ነበር። አንድ ከፍተኛ የአሜሪካ ባለስልጣን እንዳሉት፣ ይህ የትጥቅ ማስፈታት እቅድ እስራኤል ቀደም ብላ የተቀበለችው የትራምፕ የ20 ነጥብ የሰላም እቅድ አካል በመሆኑ፣ እስራኤል እቅዱን የምታደናቅፍ ከሆነ ትራምፕ በኢየሩሳሌም ላይ እጅግ እንደሚያዝኑ ተናግረዋል።
ይህንን ተከትሎ የሰላም ቦርዱ ከፍተኛ ልዑካን ኔታንያሁን ለማሳመን ሰኞ ዕለት ወደ ኢየሩሳሌም ያቀኑ ቢሆንም፣ ጥረታቸው ፍሬ አላፈራም። ቦርዱ ለእስራኤል በሚያደላ መልኩ የእቅዱን ማሻሻያ ለማድረግ ፍንጭ ቢያሳይም፣ የእስራኤልን ፍላጎት ለማስተናገድ መሞከር ወራት የፈጀውን የሀማስን ስምምነት ሊያሳጣ ይችላል የሚል ስጋት ተፈጥሯል።
በሌላ በኩል ማክሰኞ ዕለት፣ የሀማስ ከፍተኛ ባለስልጣን ጋዚ ሃማድ "ፒርስ ሞርጋን አንሴንሰርድ" በተሰኘው ታዋቂ ፕሮግራም ላይ ቀርበው ባደረጉት ቃለ ምልልስ፣ ጥቅምት 7 ቀን 2023 እስራኤል ላይ ባደረሱት ጥቃት ንፁሃንን ኢላማ እንዳላደረጉ መናገራቸው አነጋጋሪ ሆኗል። አብዛኛዎቹ አሰቃቂ ድርጊቶች በራሳቸው በታጣቂዎቹ ካሜራ የተቀረፁ ቢሆንም፣ ሃማድ "ምናልባት አንዳንድ ስህተቶች ተፈጥረው ሊሆን ይችላል" ከማለት ውጪ የንፁሃንን ግድያ አስተባብለዋል።
የ9 ወር ህፃን የነበረውን ክፊር ቢባስን ጨምሮ ስለታገቱ ቤተሰቦች በጋዜጠኛው በተጠየቁበት ወቅትም፣ በጦርነቱ መጀመሪያ ሀማስ ንፁሃንን ለመልቀቅ አቅርቦት የነበረውን ሀሳብ እስራኤል ውድቅ አድርጋዋለች ሲሉ ተሟግተዋል። ይሁን እንጂ በወቅቱ እስራኤል ታጋቾች ያለምንም ቅድመ ሁኔታ እንዲለቀቁ ስትጠይቅ፣ ሀማስ በበኩሉ በሺህ የሚቆጠሩ እስረኞች እንዲለቀቁ እና ጦርነቱ እንዲቆም ቅድመ ሁኔታ ማስቀመጡ ይታወሳል። ጋዜጠኛው የሙዚቃ ድግስ ላይ የነበሩ በመቶዎች የሚቆጠሩ ንፁሃን ለምን እንደተገደሉ ላነሳው ጥያቄ፣ ሃማድ "እሱ በእቅዳችን ውስጥ አልነበረም" ሲሉ ምላሽ ሰጥተዋል።
ይህ የኔታንያሁ አቋም እስራኤል በጋዛ ወደነበረው የመጀመሪያው "ቢጫ መስመር" እንድትመለስ ከሚጠይቀው የአሜሪካ ድጋፍ ካለው የትጥቅ ማስፈታት እቅድ ጋር የሚቃረን ነው። እስራኤል በጥቅምት 2025 ከሀማስ ጋር በተደረገው የተኩስ አቁም እና ታጋቾችን የመልቀቅ ስምምነት መሰረት ወደዚህ መስመር አፈግፍጋ የነበረ ቢሆንም፣ ከዚያን ጊዜ ወዲህ ግን በሰርጡ ላይ ያላትን የቁጥጥር ድርሻ ከ53 በመቶ ወደ 60 በመቶ አሳድጋለች። የሰላም ቦርዱ ሀማስ መሳሪያውን ማስረከብ እስኪጀምር ድረስ እስራኤል ከቢጫው መስመር በላይ ማፈግፈግ እንደማይጠበቅባት ቢያመለክትም፣ ኔታንያሁ ግን የእስራኤል ጦር አሁን ካለበት ቦታ ንቅንቅ እንደማይል አስታውቀዋል።
ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ እና ቡድናቸው የሀማስን ትጥቅ ማስፈታት እንደሚችሉ በማሰብ ረቂቅ እቅድ እንደላኩላቸው የገለጹት ኔታንያሁ፣ እስራኤል ግን እቅዱን ሳትቀበል የራሷን ማስተካከያ መልሳ መላኳን አስረድተዋል። ይሁን እንጂ ይህ ረቂቅ በአሜሪካ፣ ግብፅ፣ ኳታር፣ ቱርክ እና ሀማስ መካከል በተደረገ የተናጠል ድርድር የተገኘ በመሆኑ ከእስራኤል ጋር ለድርድር ክፍት ይሆናል ተብሎ አልተጠበቀም ነበር። አንድ ከፍተኛ የአሜሪካ ባለስልጣን እንዳሉት፣ ይህ የትጥቅ ማስፈታት እቅድ እስራኤል ቀደም ብላ የተቀበለችው የትራምፕ የ20 ነጥብ የሰላም እቅድ አካል በመሆኑ፣ እስራኤል እቅዱን የምታደናቅፍ ከሆነ ትራምፕ በኢየሩሳሌም ላይ እጅግ እንደሚያዝኑ ተናግረዋል።
ይህንን ተከትሎ የሰላም ቦርዱ ከፍተኛ ልዑካን ኔታንያሁን ለማሳመን ሰኞ ዕለት ወደ ኢየሩሳሌም ያቀኑ ቢሆንም፣ ጥረታቸው ፍሬ አላፈራም። ቦርዱ ለእስራኤል በሚያደላ መልኩ የእቅዱን ማሻሻያ ለማድረግ ፍንጭ ቢያሳይም፣ የእስራኤልን ፍላጎት ለማስተናገድ መሞከር ወራት የፈጀውን የሀማስን ስምምነት ሊያሳጣ ይችላል የሚል ስጋት ተፈጥሯል።
በሌላ በኩል ማክሰኞ ዕለት፣ የሀማስ ከፍተኛ ባለስልጣን ጋዚ ሃማድ "ፒርስ ሞርጋን አንሴንሰርድ" በተሰኘው ታዋቂ ፕሮግራም ላይ ቀርበው ባደረጉት ቃለ ምልልስ፣ ጥቅምት 7 ቀን 2023 እስራኤል ላይ ባደረሱት ጥቃት ንፁሃንን ኢላማ እንዳላደረጉ መናገራቸው አነጋጋሪ ሆኗል። አብዛኛዎቹ አሰቃቂ ድርጊቶች በራሳቸው በታጣቂዎቹ ካሜራ የተቀረፁ ቢሆንም፣ ሃማድ "ምናልባት አንዳንድ ስህተቶች ተፈጥረው ሊሆን ይችላል" ከማለት ውጪ የንፁሃንን ግድያ አስተባብለዋል።
የ9 ወር ህፃን የነበረውን ክፊር ቢባስን ጨምሮ ስለታገቱ ቤተሰቦች በጋዜጠኛው በተጠየቁበት ወቅትም፣ በጦርነቱ መጀመሪያ ሀማስ ንፁሃንን ለመልቀቅ አቅርቦት የነበረውን ሀሳብ እስራኤል ውድቅ አድርጋዋለች ሲሉ ተሟግተዋል። ይሁን እንጂ በወቅቱ እስራኤል ታጋቾች ያለምንም ቅድመ ሁኔታ እንዲለቀቁ ስትጠይቅ፣ ሀማስ በበኩሉ በሺህ የሚቆጠሩ እስረኞች እንዲለቀቁ እና ጦርነቱ እንዲቆም ቅድመ ሁኔታ ማስቀመጡ ይታወሳል። ጋዜጠኛው የሙዚቃ ድግስ ላይ የነበሩ በመቶዎች የሚቆጠሩ ንፁሃን ለምን እንደተገደሉ ላነሳው ጥያቄ፣ ሃማድ "እሱ በእቅዳችን ውስጥ አልነበረም" ሲሉ ምላሽ ሰጥተዋል።
1 day ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የጓቲማላው አስፈሪው 'ፉዌጎ' እሳተ ገሞራ ሰኞ ዕለት ዳግም በማፈንዳቱ፣ የሚመለከታቸው ባለሥልጣናት በአካባቢው የሚኖሩ ነዋሪዎች በአስቸኳይ አካባቢውን ለቀው እንዲወጡ ትዕዛዝ አስተላልፈዋል።
ሰኞ ማለዳ ላይ የተከሰተው ይኸው ፍንዳታ፣ መሸት ሲል ይበልጥ እየተባባሰ መጥቷል። ከተከሰተው አደጋ የተነሱ ፎቶግራፎች እንደሚያሳዩት፣ እሳተ ገሞራው የሚያቃጥል ፍም እና ግዙፍ የአመድ ደመናን ወደ 4 ማይል ያህል ርቀት ወደ ሰማይ ሲተፋ ይታያል። ማክሰኞ ማለዳ ላይ በቀጥታ የተላለፉ ምስሎችም ከእሳተ ገሞራው በላይ ግዙፍ የጋዝና የአመድ ደመናዎች ተከማችተው መኖራቸውን አሳይተዋል።
የጓቲማላው የአደጋ መከላከልና ማስተባበሪያ ኤጀንሲ ሰኞ ዕለት በሀገር አቀፍ ደረጃ 'የብርቱካናማ' (Orange Alert) የጥንቃቄ ማሳሰቢያ አውጥቷል። ይህ የጥንቃቄ ደረጃ፣ ከፍተኛውንና እጅግ አደገኛውን የድንገተኛ ጊዜ አደጋ ከሚያመለክተው 'ቀይ' ማሳሰቢያ በአንድ ደረጃ ብቻ ዝቅ ያለ ነው።
ይህንን ተከትሎም፣ ከዋና ከተማዋ ጓቲማላ ሲቲ 22 ማይል ርቀት ላይ በሚገኘው እሳተ ገሞራ አቅራቢያ የሚገኙ ሁለት መንደሮችን ባለሥልጣናት ሰኞ ዕለት ማስለቀቅ ጀምረዋል።
በድንገተኛ አደጋ መከላከያ አገልግሎቶች የተለቀቁ ተንቀሳቃሽ ምስሎች፣ ይህ ኃይለኛ ፍንዳታ የሰማዩን ደመና ወደ ቀይ ቀለም ሲቀይረው እና የሚያቃጥለው እሳተ ገሞራ 12,346 ጫማ ከፍታ ካለው ተራራ ቁልቁል ሲወርድ በሚዘገንን ሁኔታ ያሳያሉ።
ኤጀንሲው ማክሰኞ ዕለት ባወጣው የዜና ማሳሰቢያ ላይ "እነዚህ ቁልቁል የሚወርዱ ፍሰቶች የሞቁ የእሳተ ገሞራ ጋዞች፣ አመድ፣ ዓለቶች እና ከፍተኛ ሙቀቶች ስብስብ ሲሆኑ፣ ከተራራው ቁልቁል በከፍተኛ ፍጥነት የሚምዘገዘጉ ናቸው" ሲል አስጠንቅቋል።
በተጨማሪም በአካባቢው በሚገኙ ማህበረሰቦች ላይ የአመድ ዝናብ ሊወርድ እንደሚችል ባለሥልጣናቱ ጥብቅ ማሳሰቢያ ሰጥተዋል።
ሰኞ ማለዳ ላይ የተከሰተው ይኸው ፍንዳታ፣ መሸት ሲል ይበልጥ እየተባባሰ መጥቷል። ከተከሰተው አደጋ የተነሱ ፎቶግራፎች እንደሚያሳዩት፣ እሳተ ገሞራው የሚያቃጥል ፍም እና ግዙፍ የአመድ ደመናን ወደ 4 ማይል ያህል ርቀት ወደ ሰማይ ሲተፋ ይታያል። ማክሰኞ ማለዳ ላይ በቀጥታ የተላለፉ ምስሎችም ከእሳተ ገሞራው በላይ ግዙፍ የጋዝና የአመድ ደመናዎች ተከማችተው መኖራቸውን አሳይተዋል።
የጓቲማላው የአደጋ መከላከልና ማስተባበሪያ ኤጀንሲ ሰኞ ዕለት በሀገር አቀፍ ደረጃ 'የብርቱካናማ' (Orange Alert) የጥንቃቄ ማሳሰቢያ አውጥቷል። ይህ የጥንቃቄ ደረጃ፣ ከፍተኛውንና እጅግ አደገኛውን የድንገተኛ ጊዜ አደጋ ከሚያመለክተው 'ቀይ' ማሳሰቢያ በአንድ ደረጃ ብቻ ዝቅ ያለ ነው።
ይህንን ተከትሎም፣ ከዋና ከተማዋ ጓቲማላ ሲቲ 22 ማይል ርቀት ላይ በሚገኘው እሳተ ገሞራ አቅራቢያ የሚገኙ ሁለት መንደሮችን ባለሥልጣናት ሰኞ ዕለት ማስለቀቅ ጀምረዋል።
በድንገተኛ አደጋ መከላከያ አገልግሎቶች የተለቀቁ ተንቀሳቃሽ ምስሎች፣ ይህ ኃይለኛ ፍንዳታ የሰማዩን ደመና ወደ ቀይ ቀለም ሲቀይረው እና የሚያቃጥለው እሳተ ገሞራ 12,346 ጫማ ከፍታ ካለው ተራራ ቁልቁል ሲወርድ በሚዘገንን ሁኔታ ያሳያሉ።
ኤጀንሲው ማክሰኞ ዕለት ባወጣው የዜና ማሳሰቢያ ላይ "እነዚህ ቁልቁል የሚወርዱ ፍሰቶች የሞቁ የእሳተ ገሞራ ጋዞች፣ አመድ፣ ዓለቶች እና ከፍተኛ ሙቀቶች ስብስብ ሲሆኑ፣ ከተራራው ቁልቁል በከፍተኛ ፍጥነት የሚምዘገዘጉ ናቸው" ሲል አስጠንቅቋል።
በተጨማሪም በአካባቢው በሚገኙ ማህበረሰቦች ላይ የአመድ ዝናብ ሊወርድ እንደሚችል ባለሥልጣናቱ ጥብቅ ማሳሰቢያ ሰጥተዋል።
1 day ago
ሰላም፥ እንደምን አደራችሁ?
ምክክር ለተሻለ ብሔራዊ መግባባት
ሀገራዊ ምክክር ከመጠፋፋት ወደ ሰለጠነ፣ ሰላማዊ እና አካታች ሀገራዊ አውድ ለመሸጋገር የወቅቱ ታሪካዊ እድል ነው።
ኢትዮጵያ እያካሄደች ያለችው የሀገራዊ የምክክር ጉባኤ በጥልቀት ሲታይ ምክክር ከመረጃ ልውውጥ ያለፈ ሰዋዊነትን የሚያገናኝ ድልድይ ነው።
ዛሬ ኢትዮጵያ በብሔራዊ ደረጃ በሚደረግ የታሪክ አዲስ ምዕራፍ እና የታላቅ ምክክር ሂደት ላይ በምትገኝበት በዚህ ወቅት የምክክርን እውነተኛ ምንነትና ጥበብ መረዳት ለአንድትንና ለዘላቂ ሰላም መሰረት ነው።
ሰዎች ወደ ምክክር ሲመጡ ሃሳብን፣ ስብራትን፣ ፍርሃትንና ተስፋን ያለ ስጋት በጠረጴዛ ላይ ዘርግቶ የማየት ነጻነት ከመስጠት ባሻገር ለጥያቄዎቻቸው መልስ እንዲያገኙ መንገድ ያሳያል፡፡
የሀገራዊ ምክክር መድረክ ግብ አሸናፊና ተሸናፊ መፍጠር ሳይሆን፤ የጋራ ተስፋዎችንንና ስጋቶችንን በግልጽነት የመጋራት ነጻነትን በመጎናጸፍ የጋራ መፍትሔ መፈለግ ነው።
ምክክሩ እርስ በእርስ ለመደማመጥ ክፍት በመሆን የሌላውን ህመም እና እይታ እንደራስ አድርጎ ለመገንዘብ በር ይከፈታል።
ምክክር የራስን ሃሳብ በሌላ ሰው ድምጽ እና እይታ ለመመልከት የሚያደርግ ሲሆን፤ በሀገራዊ ሂደትም የታሪክና የፖለቲካ ብዥታዎች መልክ የሚይዙት በጋራ በመመካር እና ሌላውን እይታ በማክበር ጨጭምር ነው፡፡
ምክክር ማለት በጨለማ ውስጥ መንገድ የሚጠቁም መብራት ሲሆን መፍትሔውም በጋራ ስምምነት ላይ የተመሰረተ ይሆናል፡፡
መጠየቅ፣ መመካከርና ከሌሎች እይታ መማር የደካማነት ሳይሆን፤ የላቀ ብስለትና የጥበብ ምልክት ነው።
ኢትዮጵያ የብሔራዊ ምክክር በምታደርግበት በዚህ ወቅት ይህን የምክክር ጥበብ በመተግበር፣ በመደማመጥ፣ በግልጽነትና በቅንነት ወደተሻለ ሀገራዊ መግባባትና ዘላቂ ሰላም የመሸጋገር መንገድ ጀምራለች።
ምክክር ለተሻለ ብሔራዊ መግባባት
ሀገራዊ ምክክር ከመጠፋፋት ወደ ሰለጠነ፣ ሰላማዊ እና አካታች ሀገራዊ አውድ ለመሸጋገር የወቅቱ ታሪካዊ እድል ነው።
ኢትዮጵያ እያካሄደች ያለችው የሀገራዊ የምክክር ጉባኤ በጥልቀት ሲታይ ምክክር ከመረጃ ልውውጥ ያለፈ ሰዋዊነትን የሚያገናኝ ድልድይ ነው።
ዛሬ ኢትዮጵያ በብሔራዊ ደረጃ በሚደረግ የታሪክ አዲስ ምዕራፍ እና የታላቅ ምክክር ሂደት ላይ በምትገኝበት በዚህ ወቅት የምክክርን እውነተኛ ምንነትና ጥበብ መረዳት ለአንድትንና ለዘላቂ ሰላም መሰረት ነው።
ሰዎች ወደ ምክክር ሲመጡ ሃሳብን፣ ስብራትን፣ ፍርሃትንና ተስፋን ያለ ስጋት በጠረጴዛ ላይ ዘርግቶ የማየት ነጻነት ከመስጠት ባሻገር ለጥያቄዎቻቸው መልስ እንዲያገኙ መንገድ ያሳያል፡፡
የሀገራዊ ምክክር መድረክ ግብ አሸናፊና ተሸናፊ መፍጠር ሳይሆን፤ የጋራ ተስፋዎችንንና ስጋቶችንን በግልጽነት የመጋራት ነጻነትን በመጎናጸፍ የጋራ መፍትሔ መፈለግ ነው።
ምክክሩ እርስ በእርስ ለመደማመጥ ክፍት በመሆን የሌላውን ህመም እና እይታ እንደራስ አድርጎ ለመገንዘብ በር ይከፈታል።
ምክክር የራስን ሃሳብ በሌላ ሰው ድምጽ እና እይታ ለመመልከት የሚያደርግ ሲሆን፤ በሀገራዊ ሂደትም የታሪክና የፖለቲካ ብዥታዎች መልክ የሚይዙት በጋራ በመመካር እና ሌላውን እይታ በማክበር ጨጭምር ነው፡፡
ምክክር ማለት በጨለማ ውስጥ መንገድ የሚጠቁም መብራት ሲሆን መፍትሔውም በጋራ ስምምነት ላይ የተመሰረተ ይሆናል፡፡
መጠየቅ፣ መመካከርና ከሌሎች እይታ መማር የደካማነት ሳይሆን፤ የላቀ ብስለትና የጥበብ ምልክት ነው።
ኢትዮጵያ የብሔራዊ ምክክር በምታደርግበት በዚህ ወቅት ይህን የምክክር ጥበብ በመተግበር፣ በመደማመጥ፣ በግልጽነትና በቅንነት ወደተሻለ ሀገራዊ መግባባትና ዘላቂ ሰላም የመሸጋገር መንገድ ጀምራለች።
Sponsored by
Surafel
2 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የስሪላንካ የወንጀል ምርመራ ዲፓርትመንት በካናዳ የተሻለ የስራ ዕድል እንደሚፈጥርላቸው በማታለል ሦስት ዜጎችን በህገወጥ መንገድ ወደ ኢትዮጵያ በማዘዋወር የተጠረጠረን አንድ ስሪላንካዊ በቁጥጥር ስር ማዋሉን አስታወቀ።
ተጎጂዎቹ ዕድሜያቸው ከ25 እስከ 27 የሆኑ የኪሊኖቺ አካባቢ ነዋሪዎች ሲሆኑ፣ የውጭ ሀገር የስራ ዕድል ቃል ተገብቶላቸው በዱባይ አድርገው ወደ ኢትዮጵያ እንዲገቡ ተደርጓል። የወንጀል ምርመራ ዲፓርትመንቱ እንዳስረዳው፣ ተጠርጣሪው ለአውሮፕላን ትኬት እና ለቪዛ በሚል ከተጎጂዎቹ 6.4 ሚሊዮን የስሪላንካ ሩፒ (የገንዘብ መጠን) ተቀብሏል። ይሁን እንጂ ተጎጂዎቹ ኢትዮጵያ ውስጥ ሲደርሱ በተደራጀ ወንጀለኛ ቡድን ታግተው፣ እያንዳንዳቸውን ለመልቀቅ 30 ሺህ የአሜሪካን ዶላር ቤዛ ተጠይቆባቸዋል።
የፖሊስ ሚዲያ ክፍል እንዳብራራው፣ አጋቾቹ ይህንን የቤዛ ገንዘብ ጥያቄ ለተጎጂ ቤተሰቦች ያደረሱት ጉዞውን ባመቻቸው በዚሁ ግለሰብ በኩል ሲሆን፣ ቤተሰቦቹም ከ20 ሚሊዮን ሩፒ በላይ ከፍለዋል ተብሏል። ሜይ 27 ቀን 2026 በመከላከያ ሚኒስቴር በኩል የቀረበውን አቤቱታ ተከትሎ፣ የህገወጥ የሰዎች ዝውውር እና የባህር ላይ ወንጀል ምርመራ ክፍል ሰፊ ማጣራት ጀምሮ ነበር። ለዚህ ምርመራ በኢትዮጵያ የሚገኘው የስሪላንካ ኤምባሲ እና የኢትዮጵያ የፀጥታ አካላት ከፍተኛ ትብብር ማድረጋቸው ተገልጿል።
የተደረገውን ክትትል ተከትሎ የኢትዮጵያ የፀጥታ አካላት ሦስቱን ስሪላንካውያን በሰላም ከማስለቀቃቸውም በላይ፣ ከዚህ የተደራጀ ወንጀል ጋር ግንኙነት አላቸው የተባሉ አራት ፓኪስታናውያን እና አንድ ኢትዮጵያዊን በቁጥጥር ስር አውለዋል። በስሪላንካ በኩልም የተጎጂዎቹን ጉዞ ሲያመቻች የነበረው እና የኪሊኖቺ ነዋሪ የሆነው ተጠርጣሪ በቁጥጥር ስር ውሏል።
በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ የሚገኘው የስሪላንካ ኤምባሲ ኃላፊዎች አስፈላጊውን ማጣራት ካደረጉ በኋላ፣ ተጎጂዎቹ ወደ ሀገራቸው እንዲመለሱ እየተደረገ ይገኛል። የስሪላንካ የወንጀል ምርመራ ዲፓርትመንትም በቁጥጥር ስር በዋለው ግለሰብ እና በወንጀለኞች መረቡ መካከል ያለውን ሰፋ ያለ ትስስር ለማጋለጥ ምርመራውን አጠናክሮ ቀጥሏል።
ተጎጂዎቹ ዕድሜያቸው ከ25 እስከ 27 የሆኑ የኪሊኖቺ አካባቢ ነዋሪዎች ሲሆኑ፣ የውጭ ሀገር የስራ ዕድል ቃል ተገብቶላቸው በዱባይ አድርገው ወደ ኢትዮጵያ እንዲገቡ ተደርጓል። የወንጀል ምርመራ ዲፓርትመንቱ እንዳስረዳው፣ ተጠርጣሪው ለአውሮፕላን ትኬት እና ለቪዛ በሚል ከተጎጂዎቹ 6.4 ሚሊዮን የስሪላንካ ሩፒ (የገንዘብ መጠን) ተቀብሏል። ይሁን እንጂ ተጎጂዎቹ ኢትዮጵያ ውስጥ ሲደርሱ በተደራጀ ወንጀለኛ ቡድን ታግተው፣ እያንዳንዳቸውን ለመልቀቅ 30 ሺህ የአሜሪካን ዶላር ቤዛ ተጠይቆባቸዋል።
የፖሊስ ሚዲያ ክፍል እንዳብራራው፣ አጋቾቹ ይህንን የቤዛ ገንዘብ ጥያቄ ለተጎጂ ቤተሰቦች ያደረሱት ጉዞውን ባመቻቸው በዚሁ ግለሰብ በኩል ሲሆን፣ ቤተሰቦቹም ከ20 ሚሊዮን ሩፒ በላይ ከፍለዋል ተብሏል። ሜይ 27 ቀን 2026 በመከላከያ ሚኒስቴር በኩል የቀረበውን አቤቱታ ተከትሎ፣ የህገወጥ የሰዎች ዝውውር እና የባህር ላይ ወንጀል ምርመራ ክፍል ሰፊ ማጣራት ጀምሮ ነበር። ለዚህ ምርመራ በኢትዮጵያ የሚገኘው የስሪላንካ ኤምባሲ እና የኢትዮጵያ የፀጥታ አካላት ከፍተኛ ትብብር ማድረጋቸው ተገልጿል።
የተደረገውን ክትትል ተከትሎ የኢትዮጵያ የፀጥታ አካላት ሦስቱን ስሪላንካውያን በሰላም ከማስለቀቃቸውም በላይ፣ ከዚህ የተደራጀ ወንጀል ጋር ግንኙነት አላቸው የተባሉ አራት ፓኪስታናውያን እና አንድ ኢትዮጵያዊን በቁጥጥር ስር አውለዋል። በስሪላንካ በኩልም የተጎጂዎቹን ጉዞ ሲያመቻች የነበረው እና የኪሊኖቺ ነዋሪ የሆነው ተጠርጣሪ በቁጥጥር ስር ውሏል።
በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ የሚገኘው የስሪላንካ ኤምባሲ ኃላፊዎች አስፈላጊውን ማጣራት ካደረጉ በኋላ፣ ተጎጂዎቹ ወደ ሀገራቸው እንዲመለሱ እየተደረገ ይገኛል። የስሪላንካ የወንጀል ምርመራ ዲፓርትመንትም በቁጥጥር ስር በዋለው ግለሰብ እና በወንጀለኞች መረቡ መካከል ያለውን ሰፋ ያለ ትስስር ለማጋለጥ ምርመራውን አጠናክሮ ቀጥሏል።
2 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) በፌንቴክ የኢንቨስትመንት ማጭበርበር ወንጀል ተጠርጥረው በዋስትና ላይ የሚገኙት እነ አርቲስት ሰራዊት ፍቅሬ ጉዳይ አሁን ወደ ሌላ አሳሳቢ ደረጃ ተሸጋግሯል! አርቲስቶቹ በእጃቸው ላይ ያለውን የፍርድ ቤት ሂደት ወደ ሚዲያ በማውጣታቸው ያልታሰበ አደጋ አንዣቦባቸዋል።
ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው ሚስጥራዊ ምንጮች ለዘ-ሐበሻ እንደጠቆሙት፣ አቃቤ ህግ ይህንን የሚዲያ ላይ ቃለ-ምልልስ ተከትሎ ነገ ረቡዕ (ሐምሌ 29 ቀን) በሚኖረው ችሎት "የተሰጣቸው የዋስትና መብት ይነሳልኝ" የሚል ከባድ አቤቱታ ያቀርባል ተብሎ እየተጠበቀ ነው። ይህ ማለት ጥያቄው ተቀባይነት ካገኘ አርቲስቶቹ ዳግም ወደ እስር ቤት ሊመለሱ ይችላሉ ማለት ነው።
ነገሩ በዚህ ብቻ አላበቃም፤ ቃለ-ምልልሱ ወደ አየር ከመውጣቱ አስቀድሞ፣ ተጠርጣሪዎቹ "በከፍተኛው ፍርድ ቤት የታገደብን የባንክ ሂሳብ ይለቀቅልን" የሚል ጥያቄ ለችሎቱ አቅርበው ነበር። ፍርድ ቤቱም ጥያቄውን ከተመለከተ በኋላ፣ አቃቤ ህግ በዚህ የገንዘብ መለቀቅ አቤቱታ ላይ የራሱን አስተያየት ይዞ ሐምሌ 29 ቀን ፍርድ ቤት እንዲቀርብ ትዕዛዝ ሰጥቷል።
አርቲስቶቹ የታገደባቸውን ገንዘብ አስለቅቀው በነጻነት መንቀሳቀሳቸውን ይቀጥላሉ? ወይስ የሚዲያ ላይ ቆይታቸው ዋጋ አስከፍሏቸው ዋስትናቸው ተነጥቆ ከባድ ኪሳራ ውስጥ ይገባሉ? ነገ ረቡዕ የሚሰጠው የፍርድ ቤት ውሳኔ የጉዳዩን የመጨረሻ እልባት የሚያሳይ ይሆናል!
ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው ሚስጥራዊ ምንጮች ለዘ-ሐበሻ እንደጠቆሙት፣ አቃቤ ህግ ይህንን የሚዲያ ላይ ቃለ-ምልልስ ተከትሎ ነገ ረቡዕ (ሐምሌ 29 ቀን) በሚኖረው ችሎት "የተሰጣቸው የዋስትና መብት ይነሳልኝ" የሚል ከባድ አቤቱታ ያቀርባል ተብሎ እየተጠበቀ ነው። ይህ ማለት ጥያቄው ተቀባይነት ካገኘ አርቲስቶቹ ዳግም ወደ እስር ቤት ሊመለሱ ይችላሉ ማለት ነው።
ነገሩ በዚህ ብቻ አላበቃም፤ ቃለ-ምልልሱ ወደ አየር ከመውጣቱ አስቀድሞ፣ ተጠርጣሪዎቹ "በከፍተኛው ፍርድ ቤት የታገደብን የባንክ ሂሳብ ይለቀቅልን" የሚል ጥያቄ ለችሎቱ አቅርበው ነበር። ፍርድ ቤቱም ጥያቄውን ከተመለከተ በኋላ፣ አቃቤ ህግ በዚህ የገንዘብ መለቀቅ አቤቱታ ላይ የራሱን አስተያየት ይዞ ሐምሌ 29 ቀን ፍርድ ቤት እንዲቀርብ ትዕዛዝ ሰጥቷል።
አርቲስቶቹ የታገደባቸውን ገንዘብ አስለቅቀው በነጻነት መንቀሳቀሳቸውን ይቀጥላሉ? ወይስ የሚዲያ ላይ ቆይታቸው ዋጋ አስከፍሏቸው ዋስትናቸው ተነጥቆ ከባድ ኪሳራ ውስጥ ይገባሉ? ነገ ረቡዕ የሚሰጠው የፍርድ ቤት ውሳኔ የጉዳዩን የመጨረሻ እልባት የሚያሳይ ይሆናል!
2 days ago
ወደ ዘላቂ ልማት የሚደረግ ሽግግር
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 28፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ኢትዮጵያ ለመዋቅራዊ ሽግግር፣ ለኢኮኖሚ ጥንካሬ እና ለአካታች ሀገራዊ እድገት ቁርጠኝነት ባለው ሥርዓት እየተመራች በዘመናዊ ታሪክ ግንባታዋ ወሳኝ ምዕራፍ ላይ ትገኛለች።
በሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ ኢትዮጵያ በዋና ዋና ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ዘርፎች ላይ አበይት ስኬቶችን እያስመዘገበች ነው፡፡
የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ መሰረት የሆነው ግብርና ወደ ቴክኖሎጂ መር ያደረገው ሽግግር ተጨባጭ ውጤት እያስመዘገበ ይገኛል፡፡
በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት እና በክላስተር እርሻ እቅዶች አማካኝነት ኢትዮጵያ የሀገር ውስጥ ምርትን በከፍተኛ ሁኔታ አሳድጋለች፡፡ይህም ከውጭ የሚገቡ ምርቶች ጥገኝነትን ቀንሷል፡፡
በሀገሪቱ በአረንጓዴ ዐሻራ ፕሮግራሞች በአትክልትና ፍራፍሬ ላይ የተደረጉ ኢንቨስትመንቶች የአየር ንብረት ተፅዕኖን ለመቋቋም ሥነ ምህዳርን ለማከም እና የኑሮ ውድነትን ለማረጋጋት የሚደረገውን ጉዞ እየደገፈ ነው፡፡
የኃይል ማመንጨት አቅምን በማሳደግ የመንገድ መረቦችን በማዘመን እና በማስተሳሰር የኢትዮጵያ የመሰረተ ልማት ገጽታ አስደናቂ ለውጥ በማድረግ፤ የሀገር ውስጥ ትስስርን እያጠናከረ ኢትዮጵያን በአህጉራዊ ነጻ ንግድ ቀጣና ስር የንግድ ማዕከል እያደረጋት ይገኛል።
በአዲስ አበባ እና በክልል ከተሞች የተካሄደው የኮሪደር ልማት የሕዝብ ቦታዎችን በመሠረታዊነት በማደስ፤ መንገዶችን በማዘመን፣ አረንጓዴ የሕዝብ ቦታዎችን በመገንባት፣ የመገልገያ መሠረተ ልማቶችን በማስፋፋት እና የንፅህና አጠባበቅ ሥርዓቶችን በማሻሻል ተስማሚ የከተማ አካባቢን እየፈጠረ ነው፡፡
ዘላቂ ኢኮኖሚ ለመገንባት ኢትዮጵያ በዲጂታል ኢትዮጵያ ስትራቴጂ አማካኝነት የዲጂታል ሽግግርን በከፍተኛ ሁኔታ እያፋጠነች ትገኛለች።
በቴሌኮሙኒኬሽን እና በፋይናንስ ዘርፍ ላይ የተደረጉ ኢንቨስትመንቶች የፋይናንስ አካታችነትን እያሳደገ ነው፡፡
የኢንዱስትሪ ፓርኮችን ለማስፋፋት የሀገር ውስጥ ማኑፋክቸሪንግን ለማነቃቃት እና ከፍተኛ ዋጋ ያላቸውን የውጭ ኢንቨስትመንቶችን ለመሳብ የሚደረጉ ጥረቶች የኤክስፖርት ገቢን በማሳደግ የሰለጠነ የሰው ሀይል መፍጠራቸውን ቀጥለዋል።
የኢኮኖሚ እድገት ያለ ማህበራዊ ልማት ትርጉም የለውምና የኢትዮጵያ መንግሥት በትምህርት፣ ጤና እና ሌሎች ዘርፎች መሠረተ ልማቶችን በማሻሻል የሰራተኛውን ክህሎት ከዘመናዊ የገበያ ፍላጎት ጋር በማጣጣም የዜጎችን ሁለንተናዊ ለውጥ ማጠናከር ተችሏል።
ኢትዮጵያ እስካሁን ላስመዘገበቻቸው ስኬቶች በዓለም አቀፍ ደረጃ የተሰጧት እውቅናዎች የበለጸገች ሉዓላዊት ሀገር ለመገንባት በሚደረገው ጥረት ውስጥ ፈተናዎች ቢኖሩም ህዝብ ከውጤት ተኮር አመራር ጋር ተቀናጅቶ ወደ ዘላቂ ልማት የሚያደርገው ጉዞ በተገቢ መስመር ላይ ስለመሆኑ ማሳያ ናቸው።
በምሕረት ደምሴ
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 28፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ኢትዮጵያ ለመዋቅራዊ ሽግግር፣ ለኢኮኖሚ ጥንካሬ እና ለአካታች ሀገራዊ እድገት ቁርጠኝነት ባለው ሥርዓት እየተመራች በዘመናዊ ታሪክ ግንባታዋ ወሳኝ ምዕራፍ ላይ ትገኛለች።
በሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ ኢትዮጵያ በዋና ዋና ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ዘርፎች ላይ አበይት ስኬቶችን እያስመዘገበች ነው፡፡
የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ መሰረት የሆነው ግብርና ወደ ቴክኖሎጂ መር ያደረገው ሽግግር ተጨባጭ ውጤት እያስመዘገበ ይገኛል፡፡
በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት እና በክላስተር እርሻ እቅዶች አማካኝነት ኢትዮጵያ የሀገር ውስጥ ምርትን በከፍተኛ ሁኔታ አሳድጋለች፡፡ይህም ከውጭ የሚገቡ ምርቶች ጥገኝነትን ቀንሷል፡፡
በሀገሪቱ በአረንጓዴ ዐሻራ ፕሮግራሞች በአትክልትና ፍራፍሬ ላይ የተደረጉ ኢንቨስትመንቶች የአየር ንብረት ተፅዕኖን ለመቋቋም ሥነ ምህዳርን ለማከም እና የኑሮ ውድነትን ለማረጋጋት የሚደረገውን ጉዞ እየደገፈ ነው፡፡
የኃይል ማመንጨት አቅምን በማሳደግ የመንገድ መረቦችን በማዘመን እና በማስተሳሰር የኢትዮጵያ የመሰረተ ልማት ገጽታ አስደናቂ ለውጥ በማድረግ፤ የሀገር ውስጥ ትስስርን እያጠናከረ ኢትዮጵያን በአህጉራዊ ነጻ ንግድ ቀጣና ስር የንግድ ማዕከል እያደረጋት ይገኛል።
በአዲስ አበባ እና በክልል ከተሞች የተካሄደው የኮሪደር ልማት የሕዝብ ቦታዎችን በመሠረታዊነት በማደስ፤ መንገዶችን በማዘመን፣ አረንጓዴ የሕዝብ ቦታዎችን በመገንባት፣ የመገልገያ መሠረተ ልማቶችን በማስፋፋት እና የንፅህና አጠባበቅ ሥርዓቶችን በማሻሻል ተስማሚ የከተማ አካባቢን እየፈጠረ ነው፡፡
ዘላቂ ኢኮኖሚ ለመገንባት ኢትዮጵያ በዲጂታል ኢትዮጵያ ስትራቴጂ አማካኝነት የዲጂታል ሽግግርን በከፍተኛ ሁኔታ እያፋጠነች ትገኛለች።
በቴሌኮሙኒኬሽን እና በፋይናንስ ዘርፍ ላይ የተደረጉ ኢንቨስትመንቶች የፋይናንስ አካታችነትን እያሳደገ ነው፡፡
የኢንዱስትሪ ፓርኮችን ለማስፋፋት የሀገር ውስጥ ማኑፋክቸሪንግን ለማነቃቃት እና ከፍተኛ ዋጋ ያላቸውን የውጭ ኢንቨስትመንቶችን ለመሳብ የሚደረጉ ጥረቶች የኤክስፖርት ገቢን በማሳደግ የሰለጠነ የሰው ሀይል መፍጠራቸውን ቀጥለዋል።
የኢኮኖሚ እድገት ያለ ማህበራዊ ልማት ትርጉም የለውምና የኢትዮጵያ መንግሥት በትምህርት፣ ጤና እና ሌሎች ዘርፎች መሠረተ ልማቶችን በማሻሻል የሰራተኛውን ክህሎት ከዘመናዊ የገበያ ፍላጎት ጋር በማጣጣም የዜጎችን ሁለንተናዊ ለውጥ ማጠናከር ተችሏል።
ኢትዮጵያ እስካሁን ላስመዘገበቻቸው ስኬቶች በዓለም አቀፍ ደረጃ የተሰጧት እውቅናዎች የበለጸገች ሉዓላዊት ሀገር ለመገንባት በሚደረገው ጥረት ውስጥ ፈተናዎች ቢኖሩም ህዝብ ከውጤት ተኮር አመራር ጋር ተቀናጅቶ ወደ ዘላቂ ልማት የሚያደርገው ጉዞ በተገቢ መስመር ላይ ስለመሆኑ ማሳያ ናቸው።
በምሕረት ደምሴ
2 days ago
ቀብር
#ethiopia | የብሔራዊ ሎተሪ አስተዳደር ዋና ሥራ አስኪያጅነትና በተለያዩ መስሪያ ቤቶች ከ40 ዓመታት በላይ በኃላፊነት ሲሠሩ የነበሩት ወይዘሮ መዓዛ ቅጣው አረፉ።
ወይዘሮ መዓዛ ቅጣው በ83 ዓመታቸው ያረፉት ሐምሌ 27 ቀን 2018 ዓ.ም. በአጋጠማቸው ድንገተኛ ሕመም ነው።
ወይዘሮ መዓዛ ቅጣው ሴቶች ከዩኒቨርሲቲ ለመመረቅና በከፍተኛ ኃላፊነት ተመድበው ለመሥራት ብርቅ በነበረበት ጊዜ በውጤት ያለፉ፣ በፋና ወጊነት በሚቆጠር አርአያነት፣ በከፍተኛ ተሳትፎ ሀገራቸውን ሲያገለግሉ ቆይተዋል።
በ1950ዎቹ መጨረሻ ከቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ በኢኮኖሚክስ የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን፣ ከዋሺንግተን ዲሲ አሜሪካን ዩኒቨርሲቲ ሁለተኛ ዲግሪያቸውን በማግኘት ለወጣት ሴቶች ምሳሌ ለመሆን የበቁ ነበሩ።
ወይዘሮ መዓዛ ቅጣው ከ40 ዓመታት በላይ በኃላፊነትና በሥራ መሪነት ባገለገሉባቸው የግልና የመንግሥት መስሪያ ቤቶች አዳዲስ የሥራ ዘዴዎችን በመቀየስና የተቀናጀ አሠራር በማስለመድ ስማቸው በመልካም ሲጠራ ቆይቷል።
በተለይም ለ19 ዓመታት በዋና ሥራ አስኪያጅነት የመሩትን የብሔራዊ ሎተሪ አስተዳደር ትርፋማ ለማድረግ፣ አሠራሩን ለማዘመንና ጠንካራ ተቋም እንዲሆን ያበረከቱት አስተዋጽኦ በጊዜው በነበሩትና ሰነድ በሚመረምሩት ዘንድ የታወቀ ነው።
እንደ ፈጣን ሎተሪ ዓይነቶቹ ከጊዜው ጋር የተጣጣሙ አሠራሮች በብሔራዊ ሎተሪ አስተዳደር እንዲለመዱና የተጠናከሩ እንዲሆኑ ያደረጉት ወይዘሮ መዓዛ ቅጣው ናቸው።
በኢትዮጵያ መድን ድርጅት፣ በኅብረት ኢንሹራንስ፣ በናይል ኢንሹራንስ፣ በብርሃን ኢንሹራንስ በመመሪያ ሥራ አስኪያጅነት እየተመደቡ ተቋሞቹ እንዲጠናከሩ ሙሉ ልምዳቸውንና ችሎታቸውን ማስተላለፋቸውን አብረዋቸው የሠሩት እየመሰከሩላቸው ነው።
ወይዘሮ መዓዛ ቅጣው ትኩረትና ጥንቃቄ ከሚጠይቀው የሥራ መደባቸው ጋር ደርበው እንደ ቤተሰብ መመሪያ ማኅበር ከአንዴም ሁለቴ፣ እንደ ቀይ መስቀል ማኅበር፣ እንደ ኢየሩሳሌም የሕፃናት ማሳደጊያ ድርጅትና በመሣሰሉት ተቋማት ለረጅም ዓመታት በቦርድ ሊቀ መንበርነትና አባልነት፣ በሥራ አስፈጻሚነትም ጭምር ሲሠሩ ቆይተዋል።
ዘለግ ላለውና ውጤታማ ለሆነ ሥራቸው የተለያዩ ሽልማቶችን አግኝተዋል።
እስከ ሕልፈታቸው ድረስ ከሥራ ሳይለዩ በጥናትና በምርምር ሥር ቆይተዋል።
የሁለት ልጆች የሆኑት ወይዘሮ መዓዛ ቅጣው የቀብር ሥነ ሥርዓት ኮተቤ በሚገኘው በመካነ ቅዱሳን ሐና ወኢያቄም ቤተ ክርስቲያን ሐሙስ ሐምሌ 30 ቀን 2018 ዓ.ም. ከቀኑ በ6:00 ሰዓት እንደሚፈጸም ቤተሰቦቻቸው ነግረውናል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#ethiopia | የብሔራዊ ሎተሪ አስተዳደር ዋና ሥራ አስኪያጅነትና በተለያዩ መስሪያ ቤቶች ከ40 ዓመታት በላይ በኃላፊነት ሲሠሩ የነበሩት ወይዘሮ መዓዛ ቅጣው አረፉ።
ወይዘሮ መዓዛ ቅጣው በ83 ዓመታቸው ያረፉት ሐምሌ 27 ቀን 2018 ዓ.ም. በአጋጠማቸው ድንገተኛ ሕመም ነው።
ወይዘሮ መዓዛ ቅጣው ሴቶች ከዩኒቨርሲቲ ለመመረቅና በከፍተኛ ኃላፊነት ተመድበው ለመሥራት ብርቅ በነበረበት ጊዜ በውጤት ያለፉ፣ በፋና ወጊነት በሚቆጠር አርአያነት፣ በከፍተኛ ተሳትፎ ሀገራቸውን ሲያገለግሉ ቆይተዋል።
በ1950ዎቹ መጨረሻ ከቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ በኢኮኖሚክስ የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን፣ ከዋሺንግተን ዲሲ አሜሪካን ዩኒቨርሲቲ ሁለተኛ ዲግሪያቸውን በማግኘት ለወጣት ሴቶች ምሳሌ ለመሆን የበቁ ነበሩ።
ወይዘሮ መዓዛ ቅጣው ከ40 ዓመታት በላይ በኃላፊነትና በሥራ መሪነት ባገለገሉባቸው የግልና የመንግሥት መስሪያ ቤቶች አዳዲስ የሥራ ዘዴዎችን በመቀየስና የተቀናጀ አሠራር በማስለመድ ስማቸው በመልካም ሲጠራ ቆይቷል።
በተለይም ለ19 ዓመታት በዋና ሥራ አስኪያጅነት የመሩትን የብሔራዊ ሎተሪ አስተዳደር ትርፋማ ለማድረግ፣ አሠራሩን ለማዘመንና ጠንካራ ተቋም እንዲሆን ያበረከቱት አስተዋጽኦ በጊዜው በነበሩትና ሰነድ በሚመረምሩት ዘንድ የታወቀ ነው።
እንደ ፈጣን ሎተሪ ዓይነቶቹ ከጊዜው ጋር የተጣጣሙ አሠራሮች በብሔራዊ ሎተሪ አስተዳደር እንዲለመዱና የተጠናከሩ እንዲሆኑ ያደረጉት ወይዘሮ መዓዛ ቅጣው ናቸው።
በኢትዮጵያ መድን ድርጅት፣ በኅብረት ኢንሹራንስ፣ በናይል ኢንሹራንስ፣ በብርሃን ኢንሹራንስ በመመሪያ ሥራ አስኪያጅነት እየተመደቡ ተቋሞቹ እንዲጠናከሩ ሙሉ ልምዳቸውንና ችሎታቸውን ማስተላለፋቸውን አብረዋቸው የሠሩት እየመሰከሩላቸው ነው።
ወይዘሮ መዓዛ ቅጣው ትኩረትና ጥንቃቄ ከሚጠይቀው የሥራ መደባቸው ጋር ደርበው እንደ ቤተሰብ መመሪያ ማኅበር ከአንዴም ሁለቴ፣ እንደ ቀይ መስቀል ማኅበር፣ እንደ ኢየሩሳሌም የሕፃናት ማሳደጊያ ድርጅትና በመሣሰሉት ተቋማት ለረጅም ዓመታት በቦርድ ሊቀ መንበርነትና አባልነት፣ በሥራ አስፈጻሚነትም ጭምር ሲሠሩ ቆይተዋል።
ዘለግ ላለውና ውጤታማ ለሆነ ሥራቸው የተለያዩ ሽልማቶችን አግኝተዋል።
እስከ ሕልፈታቸው ድረስ ከሥራ ሳይለዩ በጥናትና በምርምር ሥር ቆይተዋል።
የሁለት ልጆች የሆኑት ወይዘሮ መዓዛ ቅጣው የቀብር ሥነ ሥርዓት ኮተቤ በሚገኘው በመካነ ቅዱሳን ሐና ወኢያቄም ቤተ ክርስቲያን ሐሙስ ሐምሌ 30 ቀን 2018 ዓ.ም. ከቀኑ በ6:00 ሰዓት እንደሚፈጸም ቤተሰቦቻቸው ነግረውናል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
Sponsored by
Surafel
2 days ago
(ዘ-ሐበሻ ስፖርት) ቤርናርዶ ሲልቫን ስንመለከት እግር ኳስ ተጫዋች ሳይሆን፣ የታሸን የጥበብ መጻሕፍትን በፀጥታ የሚያነብ አርክቴክት (የኪነ-ህንፃ ባለሙያ) ነው የሚመስለው።
ለዓይን የማይጮሁ ቀለል ያሉ ቲሸርቶች፣ የሊነን አልባሳት፣ ሰፋፊ ሱሪዎች፣ የበርከንስቶክ ጫማዎች እና ከክር የተሰሩ ፖሎ ሹራቦች፤ አካላዊ ገጽታውም ሆነ አለባበሱ አንዳችም ትኩረትን አይሻም።
እንደ እውነቱ ከሆነ አእምሮው የተገራ አማካይ የግድ እንደ ፊልም ኮከብ መታየት አያስፈልገውም። በሜዳ ላይ ሁሉም ነገር በከፍተኛ ፍጥነት በሚምዘገዘግበት እና ውጥረት በነገሰበት ፍልሚያ ውስጥ፣ በእርጋታ እና በሰከነ መንፈስ ማሰብ የሚችል መሪ መሆን ብቻ በቂው ነው።
ልዩ የፈጠራ አቅም... ጥልቅ ብስለት... አስገራሚ ትዕግስት... እና ረቂቅ ስሜት!
ቤርናርዶ ሲልቫ ልክ እንደ አለባበሱ ነው የሚጫወተው። በሜዳ ላይ ታላላቅ እና ወሳኝ ነገሮች በዙሪያው እንዲከናወኑ ያደርጋል እንጂ፣ እሱ ራሱ የሁሉ ነገር ማዕከል ሆኖ ጎልቶ ለመታየት አይሞክርም። አለባበሱም፣ አጨዋወቱም — የፍፁም እርጋታ እና የጥበብ መገለጫ ነው!
ለዓይን የማይጮሁ ቀለል ያሉ ቲሸርቶች፣ የሊነን አልባሳት፣ ሰፋፊ ሱሪዎች፣ የበርከንስቶክ ጫማዎች እና ከክር የተሰሩ ፖሎ ሹራቦች፤ አካላዊ ገጽታውም ሆነ አለባበሱ አንዳችም ትኩረትን አይሻም።
እንደ እውነቱ ከሆነ አእምሮው የተገራ አማካይ የግድ እንደ ፊልም ኮከብ መታየት አያስፈልገውም። በሜዳ ላይ ሁሉም ነገር በከፍተኛ ፍጥነት በሚምዘገዘግበት እና ውጥረት በነገሰበት ፍልሚያ ውስጥ፣ በእርጋታ እና በሰከነ መንፈስ ማሰብ የሚችል መሪ መሆን ብቻ በቂው ነው።
ልዩ የፈጠራ አቅም... ጥልቅ ብስለት... አስገራሚ ትዕግስት... እና ረቂቅ ስሜት!
ቤርናርዶ ሲልቫ ልክ እንደ አለባበሱ ነው የሚጫወተው። በሜዳ ላይ ታላላቅ እና ወሳኝ ነገሮች በዙሪያው እንዲከናወኑ ያደርጋል እንጂ፣ እሱ ራሱ የሁሉ ነገር ማዕከል ሆኖ ጎልቶ ለመታየት አይሞክርም። አለባበሱም፣ አጨዋወቱም — የፍፁም እርጋታ እና የጥበብ መገለጫ ነው!
2 days ago
በመሰልቸትም ይሁን እንዲሁ ተስፋ ቆርጬ ለአመታት የለፋውበትን ፊልም ለማውጣት ሰንፌ ነበር ። በተለይ ባለፉት ሁለትና ሶስት ወራቶች በገጠመኝ ሀዘን ምክኒያት ሁሉም ነገር ድብርብር ብሎኝ ነበር ። በሆነችዋ ምርጥዬ ቀን ግን የሰራነውን ፊልም ለማየት ከሸዊት ጋር ቀጠሮ ያዝን... ፊልሙን አይተን ከጨረስን በኃላ ሸዊት ያወራችኝ ነገር... ሁሉ ነገሬን ቀየረው ! ጥቂት ለማይባሉ ወራቶች አጥቼ የነበረውን ሞራል በአንዴ መለሰችው ..! እንደዛ ቀን ፊልሜን ጨርሶ ለማውጣት ሞራል ያገኘውበት ቀን የለም ።
ሸዊት ሚዲያ ላይ እንደምታወራው በጣም ቅን ሰው ናት ። የምታወራውን የምትኖር ፀዴ ሰው ናት ። ቅንነቷን ደግነቷን ደግሞ በነበረን የስራ ግኑኝነት ሁሉ አይቼዋለው ። ከልቧ ሰው ናት ። ሰዎች ሰርተው አጊንተው እንዲሳካላቸው የምትፈልግ ሰው ናት ። በፍፁም ክፋት የሚባል ነገር አታይባትም ። ለዛም ነው እኔ ሳላውቅ በራሷ ፍቃድ ሞራልም ማስታወቂያም እንዲሆነኝ በዛሬው በሰይፉ ሾ ላይ ፊልሜን ያስተዋወቀችልኝ ።
እንዲሁ ሸዊት ስለሆነች ብቻና በቅርቡ ብር አምባር ቲያትርን ከሀገር ውጪ ለማሳየት እንደምትሄድ ስለማውቅ ፕሮግራሙን መከታተል ጀመርኩ መጨረሻ ላይ ግን በቅርቡ አዲሱ ፊልሜ ይወጣል ብላ ፊልማችንን ስታስተዋውቅ ወላሂ ገረመችኝ ፤ ምን አይነት ቅን ልብ ቢኖራት ነው በዚህ ልክ ይኼን ያህል ርቀት የምትሄደው አልኩ ። ሰይፉ ሾ ላይ የሄደችው ቲያትሩን ለማስተዋወቅ ቢሆንም በመልካምነቷና ቅን በማሰቧ ፊልማችን እንዲተዋወቅ አድርጋለች ።
ከሸዊት ጋር በነበረን ቆይታ ያሳየችኝ መልካምነት እንዳለ ሆኖ ይኼን ግን አልጠበኩም ነበር ። ሸዋዬ ሲበዛ አክባሪሽና ወዳጅ ነሽ ። ስለምትሰጪኝ ምክር ፤ ስለምትሰጪኝ ብርታት ሁሉ ከልብ አመሰግናለሁ ። በስራ ላይ ሌላ ስራ ያስደጋግመን ። ከዚህም በላይ ካንቺ ጋር ለመስራት ያብቃን 👐
"ወንዶቹ አልተወለዱም " በቅርቡ ለእናተም የሚደርስ ይሆናል ..!
ሸዊት ሚዲያ ላይ እንደምታወራው በጣም ቅን ሰው ናት ። የምታወራውን የምትኖር ፀዴ ሰው ናት ። ቅንነቷን ደግነቷን ደግሞ በነበረን የስራ ግኑኝነት ሁሉ አይቼዋለው ። ከልቧ ሰው ናት ። ሰዎች ሰርተው አጊንተው እንዲሳካላቸው የምትፈልግ ሰው ናት ። በፍፁም ክፋት የሚባል ነገር አታይባትም ። ለዛም ነው እኔ ሳላውቅ በራሷ ፍቃድ ሞራልም ማስታወቂያም እንዲሆነኝ በዛሬው በሰይፉ ሾ ላይ ፊልሜን ያስተዋወቀችልኝ ።
እንዲሁ ሸዊት ስለሆነች ብቻና በቅርቡ ብር አምባር ቲያትርን ከሀገር ውጪ ለማሳየት እንደምትሄድ ስለማውቅ ፕሮግራሙን መከታተል ጀመርኩ መጨረሻ ላይ ግን በቅርቡ አዲሱ ፊልሜ ይወጣል ብላ ፊልማችንን ስታስተዋውቅ ወላሂ ገረመችኝ ፤ ምን አይነት ቅን ልብ ቢኖራት ነው በዚህ ልክ ይኼን ያህል ርቀት የምትሄደው አልኩ ። ሰይፉ ሾ ላይ የሄደችው ቲያትሩን ለማስተዋወቅ ቢሆንም በመልካምነቷና ቅን በማሰቧ ፊልማችን እንዲተዋወቅ አድርጋለች ።
ከሸዊት ጋር በነበረን ቆይታ ያሳየችኝ መልካምነት እንዳለ ሆኖ ይኼን ግን አልጠበኩም ነበር ። ሸዋዬ ሲበዛ አክባሪሽና ወዳጅ ነሽ ። ስለምትሰጪኝ ምክር ፤ ስለምትሰጪኝ ብርታት ሁሉ ከልብ አመሰግናለሁ ። በስራ ላይ ሌላ ስራ ያስደጋግመን ። ከዚህም በላይ ካንቺ ጋር ለመስራት ያብቃን 👐
"ወንዶቹ አልተወለዱም " በቅርቡ ለእናተም የሚደርስ ይሆናል ..!
2 days ago
ጓቲማላ የፉዌጎ እሳተ ገሞራ ፈንድቶ ከፍተኛ የአደጋ ማንቂያ ታወጀ
#ethiopia | ጓቲማላ መንግሥት የመካከለኛው አሜሪካ እጅግ ንቁ ከሆኑ እሳተ ገሞራዎች አንዱ የሆነው ፉዌጎ (Fuego) ከባድ ፍንዳታ ካሳየ በኋላ በመላ ሀገሪቱ ሁለተኛውን ከፍተኛ የአደጋ ማንቂያ (Orange Alert) አውጇል።
ባለሥልጣናት ከእሳተ ገሞራው አቅራቢያ የሚገኙ ሁለት መንደሮችን በአስቸኳይ እንዲለቁ ትዕዛዝ ሰጥተዋል።
የላቫ ፍሰት፣ የአመድ ደመና እና ፓይሮክላስቲክ ፍሰቶች (በከፍተኛ ፍጥነት የሚንቀሳቀሱ የሞቃት ጋዝ፣ አመድ እና ድንጋይ ድብልቆች) በአካባቢው ላይ አደጋ ሊያስከትሉ ስለሚችሉ የመከላከያ እርምጃዎች ተጠናክረዋል።
በተጨማሪም በአካባቢው ያሉ ትምህርት ቤቶች ለጊዜው ተዘግተዋል፣ ወደ ታሪካዊቷ አንቲጓ ከተማ የሚያመራው ዋና መንገድም ተዘግቷል።
በአሁኑ ወቅት የሟቾች ወይም የከባድ ጉዳት ሪፖርት አልወጣም፣ ነገር ግን ባለሥልጣናት የእሳተ ገሞራውን እንቅስቃሴ በቅርብ እየተከታተሉ ነው።
ፉዌጎ እሳተ ገሞራ በ2018 በፈነዳበት ወቅት በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ሕይወታቸውን አጥተው ነበር፤ ስለዚህ የአሁኑ ፍንዳታ በባለሥልጣናት በከፍተኛ ጥንቃቄ እየተያዘ ነው።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#ethiopia | ጓቲማላ መንግሥት የመካከለኛው አሜሪካ እጅግ ንቁ ከሆኑ እሳተ ገሞራዎች አንዱ የሆነው ፉዌጎ (Fuego) ከባድ ፍንዳታ ካሳየ በኋላ በመላ ሀገሪቱ ሁለተኛውን ከፍተኛ የአደጋ ማንቂያ (Orange Alert) አውጇል።
ባለሥልጣናት ከእሳተ ገሞራው አቅራቢያ የሚገኙ ሁለት መንደሮችን በአስቸኳይ እንዲለቁ ትዕዛዝ ሰጥተዋል።
የላቫ ፍሰት፣ የአመድ ደመና እና ፓይሮክላስቲክ ፍሰቶች (በከፍተኛ ፍጥነት የሚንቀሳቀሱ የሞቃት ጋዝ፣ አመድ እና ድንጋይ ድብልቆች) በአካባቢው ላይ አደጋ ሊያስከትሉ ስለሚችሉ የመከላከያ እርምጃዎች ተጠናክረዋል።
በተጨማሪም በአካባቢው ያሉ ትምህርት ቤቶች ለጊዜው ተዘግተዋል፣ ወደ ታሪካዊቷ አንቲጓ ከተማ የሚያመራው ዋና መንገድም ተዘግቷል።
በአሁኑ ወቅት የሟቾች ወይም የከባድ ጉዳት ሪፖርት አልወጣም፣ ነገር ግን ባለሥልጣናት የእሳተ ገሞራውን እንቅስቃሴ በቅርብ እየተከታተሉ ነው።
ፉዌጎ እሳተ ገሞራ በ2018 በፈነዳበት ወቅት በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ሕይወታቸውን አጥተው ነበር፤ ስለዚህ የአሁኑ ፍንዳታ በባለሥልጣናት በከፍተኛ ጥንቃቄ እየተያዘ ነው።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
2 days ago
ብሩስ ዊሊስ ባለቤት የባለቤቷን ህመም (FTD) ለመከታተል የሚያስችል ህግ እንዲፀድቅ ግፊት አደረገች
የታዋቂው የፊልም ኮከብ ብሩስ ዊሊስ ባለቤት የሆነችው ኤማ ሄሚንግ ዊሊስ፣ ባለቤቷ የተጠቃበትን 'የፊት ለፊት የጭንቅላት ክፍል መጎዳት' (Frontotemporal Degeneration - FTD) የተሰኘውን የመርሳት ህመም የሚከታተል ህግ እንዲፀድቅ ሰኞ ዕለት በካሊፎርኒያ ካፒቶል ከሚገኙ ህግ አውጪዎች ጋር በመሆን ግፊት አድርጋለች።
በሴናተር ሮጀር ኒየሎ የተዘጋጀው እና ኤማ ሄሚንግ ዊሊስ ድጋፏን የሰጠችለት ይህ ረቂቅ ህግ፣ የካሊፎርኒያ የህዝብ ጤና መምሪያ ስለ FTD ህመም መረጃዎችን እንዲሰበስብ የሚያስገድድ ነው። መምሪያው በአሁኑ ወቅት የሃንቲንግተን፣ የፓርኪንሰንስ፣ የአልዛይመርስ እና የማልቲፕል ስክለሮሲስ በሽታዎችን መረጃዎች በመሰብሰብ ላይ ይገኛል። የህጉን ሂደት በተመለከተ፣ ረቂቅ ህጉ ሀምሌ 1 ቀን የህግ አውጪው ምክር ቤት የአንድ ወር የክረምት እረፍት ከመውጣቱ በፊት በምክር ቤቱ ተጠባባቂ መዝገብ ውስጥ ሰፍሮ ነበር። ምክር ቤቱ ሰኞ ዕለት ስራውን የጀመረ ሲሆን፣ ረቂቅ ህጎችን ለማጽደቅ የአንድ ወር ጊዜ ብቻ ቀርቶታል። ይህ የህግ ማዕቀፍ እስከ ጥር 1፣ 2032 ድረስ የሚራዘም ሲሆን፣ የህጉ ትንታኔ እንደሚያሳየው ለሰራተኞች እና ለኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ክፍያን ጨምሮ በዓመት 2.7 ሚሊዮን ዶላር በጀት ይጠይቃል።
ኤማ ሰኞ ዕለት በካፒቶል በሰጠችው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ እንዳብራራችው፣ FTDን በነርቭ መጎዳት በሽታዎች መዝገብ ውስጥ ማካተት የካሊፎርኒያ ታካሚዎችን መቁጠር ብቻ ሳይሆን፣ በካሊፎርኒያ የሚገኙ የባዮቴክ ተመራማሪዎች ህክምና እና ፈውስ ለማግኘት የሚፈልጉትን ጠቃሚ የመረጃ ቋት መገንባት ነው። ባለቤቷ ለመጀመሪያ ጊዜ በ2022 በበሽታው መያዙ እንደታወቀ የጠቀሰችው ኤማ፣ አሁን ላይ ህመሙን የሚያዘገይ ወይም የሚያቆም ህክምና እንደሌለ ብታምንም፣ የህመሙን መረጃዎች መሰብሰብ ግን ለምርምር ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳለው ተናግራለች። ታዋቂው ተዋናይ ስለሚገኝበት ሁኔታ ተጠይቃ ስትመልስም፣ በዚህ እጅግ ጨካኝ በሆነ በሽታ ውስጥ ሆኖ ማድረግ የሚችለውን ያህል በጥሩ ሁኔታ ላይ ይገኛል ብዬ አስባለሁ ስትል ገልጻለች።
'ፒክስ ዲዚዝ' በመባልም የሚታወቀው ይህ ህመም፣ ከግንባር ጀርባ ወይም ከጆሮ አካባቢ ባሉ የጭንቅላት ክፍሎች ላይ በሚከሰት የነርቭ ሴሎች መጎዳት የሚመጣ የጭንቅላት እክል ነው። የበሽታው ምልክቶች የባህሪ እና የስብዕና ለውጥን፣ ስሜት አልባ መሆንን ፣ ውሳኔ የመስጠት፣ የመንቀሳቀስ እና የመናገር ችግርን፣ እንዲሁም ቃላትን የመረዳት አቅም ማጣትን ያካትታሉ።
የኤፍ ቲ ዲ ማህበር የጥብቅና እና የበጎ ፈቃደኞች ተሳትፎ ዳይሬክተር የሆኑት ሜጋን ቡዝቢ እንደገለጹት፣ የታካሚ ቤተሰቦች እነዚህ ምልክቶች ሲታዩ ከሐኪሞች ግልጽ የሆነ ምላሽ ለማግኘት ብዙ ጊዜ ይቸገራሉ። ዳይሬክተሯ አክለውም፣ ይህ ሁኔታ ለብዙ የካሊፎርኒያ ቤተሰቦች የFTD ምርመራ ውጤትን ለማግኘት የሚያደርጉት ረጅም እና አድካሚ ጉዞ እውነታ መሆኑን አብራርተዋል። በአሁኑ ወቅት በሽታውን ለማከም የሚረዱ ህክምናዎች እጅግ ውስን ሲሆኑ፣ ፈውስም እስካሁን አልተገኘለትም።
የታዋቂው የፊልም ኮከብ ብሩስ ዊሊስ ባለቤት የሆነችው ኤማ ሄሚንግ ዊሊስ፣ ባለቤቷ የተጠቃበትን 'የፊት ለፊት የጭንቅላት ክፍል መጎዳት' (Frontotemporal Degeneration - FTD) የተሰኘውን የመርሳት ህመም የሚከታተል ህግ እንዲፀድቅ ሰኞ ዕለት በካሊፎርኒያ ካፒቶል ከሚገኙ ህግ አውጪዎች ጋር በመሆን ግፊት አድርጋለች።
በሴናተር ሮጀር ኒየሎ የተዘጋጀው እና ኤማ ሄሚንግ ዊሊስ ድጋፏን የሰጠችለት ይህ ረቂቅ ህግ፣ የካሊፎርኒያ የህዝብ ጤና መምሪያ ስለ FTD ህመም መረጃዎችን እንዲሰበስብ የሚያስገድድ ነው። መምሪያው በአሁኑ ወቅት የሃንቲንግተን፣ የፓርኪንሰንስ፣ የአልዛይመርስ እና የማልቲፕል ስክለሮሲስ በሽታዎችን መረጃዎች በመሰብሰብ ላይ ይገኛል። የህጉን ሂደት በተመለከተ፣ ረቂቅ ህጉ ሀምሌ 1 ቀን የህግ አውጪው ምክር ቤት የአንድ ወር የክረምት እረፍት ከመውጣቱ በፊት በምክር ቤቱ ተጠባባቂ መዝገብ ውስጥ ሰፍሮ ነበር። ምክር ቤቱ ሰኞ ዕለት ስራውን የጀመረ ሲሆን፣ ረቂቅ ህጎችን ለማጽደቅ የአንድ ወር ጊዜ ብቻ ቀርቶታል። ይህ የህግ ማዕቀፍ እስከ ጥር 1፣ 2032 ድረስ የሚራዘም ሲሆን፣ የህጉ ትንታኔ እንደሚያሳየው ለሰራተኞች እና ለኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ክፍያን ጨምሮ በዓመት 2.7 ሚሊዮን ዶላር በጀት ይጠይቃል።
ኤማ ሰኞ ዕለት በካፒቶል በሰጠችው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ እንዳብራራችው፣ FTDን በነርቭ መጎዳት በሽታዎች መዝገብ ውስጥ ማካተት የካሊፎርኒያ ታካሚዎችን መቁጠር ብቻ ሳይሆን፣ በካሊፎርኒያ የሚገኙ የባዮቴክ ተመራማሪዎች ህክምና እና ፈውስ ለማግኘት የሚፈልጉትን ጠቃሚ የመረጃ ቋት መገንባት ነው። ባለቤቷ ለመጀመሪያ ጊዜ በ2022 በበሽታው መያዙ እንደታወቀ የጠቀሰችው ኤማ፣ አሁን ላይ ህመሙን የሚያዘገይ ወይም የሚያቆም ህክምና እንደሌለ ብታምንም፣ የህመሙን መረጃዎች መሰብሰብ ግን ለምርምር ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳለው ተናግራለች። ታዋቂው ተዋናይ ስለሚገኝበት ሁኔታ ተጠይቃ ስትመልስም፣ በዚህ እጅግ ጨካኝ በሆነ በሽታ ውስጥ ሆኖ ማድረግ የሚችለውን ያህል በጥሩ ሁኔታ ላይ ይገኛል ብዬ አስባለሁ ስትል ገልጻለች።
'ፒክስ ዲዚዝ' በመባልም የሚታወቀው ይህ ህመም፣ ከግንባር ጀርባ ወይም ከጆሮ አካባቢ ባሉ የጭንቅላት ክፍሎች ላይ በሚከሰት የነርቭ ሴሎች መጎዳት የሚመጣ የጭንቅላት እክል ነው። የበሽታው ምልክቶች የባህሪ እና የስብዕና ለውጥን፣ ስሜት አልባ መሆንን ፣ ውሳኔ የመስጠት፣ የመንቀሳቀስ እና የመናገር ችግርን፣ እንዲሁም ቃላትን የመረዳት አቅም ማጣትን ያካትታሉ።
የኤፍ ቲ ዲ ማህበር የጥብቅና እና የበጎ ፈቃደኞች ተሳትፎ ዳይሬክተር የሆኑት ሜጋን ቡዝቢ እንደገለጹት፣ የታካሚ ቤተሰቦች እነዚህ ምልክቶች ሲታዩ ከሐኪሞች ግልጽ የሆነ ምላሽ ለማግኘት ብዙ ጊዜ ይቸገራሉ። ዳይሬክተሯ አክለውም፣ ይህ ሁኔታ ለብዙ የካሊፎርኒያ ቤተሰቦች የFTD ምርመራ ውጤትን ለማግኘት የሚያደርጉት ረጅም እና አድካሚ ጉዞ እውነታ መሆኑን አብራርተዋል። በአሁኑ ወቅት በሽታውን ለማከም የሚረዱ ህክምናዎች እጅግ ውስን ሲሆኑ፣ ፈውስም እስካሁን አልተገኘለትም።
Sponsored by
Surafel
2 days ago
ሳይታጠብ እስከ አንድ ወር የሚቆይ አዲስ ቲ-ሸርት ለገበያ ቀረበ
አሜሪካዊው የልብስ ኩባንያ ‘ሄርክሊዮን’ ያለ ምንም እጥበት እስከ አንድ ወር ድረስ መጥፎ ጠረን ሳይይዝ በየቀኑ መልበስ የሚያስችል "HercShirt V5.0" የተሰኘ አዲስ ቲ-ሸርት ለገበያ ማቅረቡን አስታውቋል።
ኩባንያው ለዚህ ፈጠራው መዳብ፣ ብር፣ ዚንክ፣ ወርቅ እና የእሳተ ገሞራ አመድን ጨምሮ ሰባት ልዩ ንጥረ ነገሮችን በጨርቁ ክር ውስጥ ማካተቱ ተገልጿል ።
እነዚህ ንጥረ ነገሮች ባክቴሪያዎችን ያግዳሉ፤ እርጥበትንም በመምጠጥ ልብሱ ምንጊዜም ይዘቱን ጠብቆ እንዲቆይ ያደርጋሉ ተብሏል።
አልፎ አልፎ ብቻ ስለሚታጠብ ከሰባት መደበኛ ቲ-ሸርቶች በላይ ያገለግላል የተባለው ይህ ምርት በ79 ዶላር ይሸጣል።
በተጨማሪም አቅማቸው አነስተኛ ለሆኑ ደንበኞች ለሶስት ቀናት የሚቆይ የ39 ዶላር አማራጭ እና እስከ ሁለት ሳምንት የሚያገለግል መደበኛ ስሪት መዘጋጀቱ ተጠቅሷል።
በቅርቡ በጥቁር ቀለም ሽያጩ የሚጀምረው ይህ ቲ-ሸርት፣ ወደፊት በሌሎች ቀለሞችም ለገበያ ይቀርባል መባሉ ተዘግቧል።
Seledadotio
Seledadotio
አሜሪካዊው የልብስ ኩባንያ ‘ሄርክሊዮን’ ያለ ምንም እጥበት እስከ አንድ ወር ድረስ መጥፎ ጠረን ሳይይዝ በየቀኑ መልበስ የሚያስችል "HercShirt V5.0" የተሰኘ አዲስ ቲ-ሸርት ለገበያ ማቅረቡን አስታውቋል።
ኩባንያው ለዚህ ፈጠራው መዳብ፣ ብር፣ ዚንክ፣ ወርቅ እና የእሳተ ገሞራ አመድን ጨምሮ ሰባት ልዩ ንጥረ ነገሮችን በጨርቁ ክር ውስጥ ማካተቱ ተገልጿል ።
እነዚህ ንጥረ ነገሮች ባክቴሪያዎችን ያግዳሉ፤ እርጥበትንም በመምጠጥ ልብሱ ምንጊዜም ይዘቱን ጠብቆ እንዲቆይ ያደርጋሉ ተብሏል።
አልፎ አልፎ ብቻ ስለሚታጠብ ከሰባት መደበኛ ቲ-ሸርቶች በላይ ያገለግላል የተባለው ይህ ምርት በ79 ዶላር ይሸጣል።
በተጨማሪም አቅማቸው አነስተኛ ለሆኑ ደንበኞች ለሶስት ቀናት የሚቆይ የ39 ዶላር አማራጭ እና እስከ ሁለት ሳምንት የሚያገለግል መደበኛ ስሪት መዘጋጀቱ ተጠቅሷል።
በቅርቡ በጥቁር ቀለም ሽያጩ የሚጀምረው ይህ ቲ-ሸርት፣ ወደፊት በሌሎች ቀለሞችም ለገበያ ይቀርባል መባሉ ተዘግቧል።
Seledadotio
Seledadotio
2 days ago
የአነስተኛ ገንዘብ ኖቶች እጥረት‼️
የአነስተኛ የገንዘብ ኖቶች እጥረት የችርቻሮ ነጋዴዎችን እና ደንበኞችን እየፈተነ ይገኛል።
በኢትዮጵያ የችርቻሮ ንግድ ዘርፍ አነስተኛ የገንዘብ ኖቶች በተለይም የ 10 ብር ኖት እጥረት በዕለታዊ የንግድ እንቅስቃሴዎች ላይ ከፍተኛ ጫና እያሳደረ ነው። በርካታ የሱቅ ባለቤቶች መልስ በማጣታቸው ምክንያት ደንበኞችን ለመመለስ ወይም እቃዎችን በዕዳ ለመስጠት ተገደዋል።
የአገሪቱ አጠቃላይ የዋጋ ንረት 13.9% እንዲሁም የምግብ ዋጋ ንረት 15.1% በመድረሱ፣ አነስተኛ ኖቶች በእጅ የመዘዋወር ፍጥነታቸው ጨምሮ በፍጥነት እንዲያልቁና እንዲቀደዱ አድርጓል። እ.ኤ.አ በ 2020 ከተደረገው የብር ቅያሬ ወዲህ አዲስ የ 10 ብር ኖት ያልታተመ በመሆኑም በገበያው ላይ ያለው መጠን በከፍተኛ ሁኔታ እየቀነሰ መጥቷል።
በተጨማሪም ከ 350 ቢሊዮን ብር በላይ ከባንክ ሥርዓት ውጭ በህዝብ እጅ ስለሚገኝ፣ ብሔራዊ ባንክ ያረጁ ኖቶችን ሰብስቦ ለመተካትና ለማስወገድ ተቸግሯል። እስከ እ.ኤ.አ 2030 ሙሉ በሙሉ ከጥሬ ገንዘብ ነፃ የመሆን ግብ ቢኖርም፣ የኤሌክትሪክ እና የቴሌኮም መቆራረጥ እንዲሁም የዲጂታል መሣሪያዎች ውድነት ሽግግሩን እያዘገየው ይገኛል።
"የአነስተኛ ኖቶች እጥረት የዘወትር ራስ ምታት ሆኖብናል። አንዳንድ ጊዜ ደንበኞችን መልሰን እንልካለን፤ ወይም ዕቃዎችን በብድር ለመስጠት እንገደዳለን።" ሲሉ ተደምጠዋል።
Seledadotio
Seledadotio
የአነስተኛ የገንዘብ ኖቶች እጥረት የችርቻሮ ነጋዴዎችን እና ደንበኞችን እየፈተነ ይገኛል።
በኢትዮጵያ የችርቻሮ ንግድ ዘርፍ አነስተኛ የገንዘብ ኖቶች በተለይም የ 10 ብር ኖት እጥረት በዕለታዊ የንግድ እንቅስቃሴዎች ላይ ከፍተኛ ጫና እያሳደረ ነው። በርካታ የሱቅ ባለቤቶች መልስ በማጣታቸው ምክንያት ደንበኞችን ለመመለስ ወይም እቃዎችን በዕዳ ለመስጠት ተገደዋል።
የአገሪቱ አጠቃላይ የዋጋ ንረት 13.9% እንዲሁም የምግብ ዋጋ ንረት 15.1% በመድረሱ፣ አነስተኛ ኖቶች በእጅ የመዘዋወር ፍጥነታቸው ጨምሮ በፍጥነት እንዲያልቁና እንዲቀደዱ አድርጓል። እ.ኤ.አ በ 2020 ከተደረገው የብር ቅያሬ ወዲህ አዲስ የ 10 ብር ኖት ያልታተመ በመሆኑም በገበያው ላይ ያለው መጠን በከፍተኛ ሁኔታ እየቀነሰ መጥቷል።
በተጨማሪም ከ 350 ቢሊዮን ብር በላይ ከባንክ ሥርዓት ውጭ በህዝብ እጅ ስለሚገኝ፣ ብሔራዊ ባንክ ያረጁ ኖቶችን ሰብስቦ ለመተካትና ለማስወገድ ተቸግሯል። እስከ እ.ኤ.አ 2030 ሙሉ በሙሉ ከጥሬ ገንዘብ ነፃ የመሆን ግብ ቢኖርም፣ የኤሌክትሪክ እና የቴሌኮም መቆራረጥ እንዲሁም የዲጂታል መሣሪያዎች ውድነት ሽግግሩን እያዘገየው ይገኛል።
"የአነስተኛ ኖቶች እጥረት የዘወትር ራስ ምታት ሆኖብናል። አንዳንድ ጊዜ ደንበኞችን መልሰን እንልካለን፤ ወይም ዕቃዎችን በብድር ለመስጠት እንገደዳለን።" ሲሉ ተደምጠዋል።
Seledadotio
Seledadotio
Comments