1 month ago
የጥበብ ዓምዱ አታኽልቲ ነጋ በአዲስ ስራ ተመለሰ
* "ውሽጥን ደገን" ሊመረቅ ነው
#ethiopia | ከሦስት አስርተ ዓመታት በላይ በትግራይ የፊልምና ድራማ ዘርፍ ላይ የማይደበዝዝ አሻራ ያሳረፈው፣ መምህር፣ ደራሲና ተዋናይ አታኽልቲ ነጋ ዳግም ወደ ስክሪን ተመልሷል።
በ"ማሾ" እና "ምትሓታዊ ዓለባ" (ብርሆን ገይፀን) የብዙዎችን ልብ የገዛው ይህ የጥበብ ሰው፣ አሁን ደግሞ "ውሽጥን ደገን" (Inside/Outside) በተሰኘ አዲስ የሲትኮም ድራማ ብቅ ብሏል።
ቀን፦
እሁድ ከሰዓት በኋላ 8፡00 ሰዓት።
ቦታ፦
በመቀለ ሰማዕታት ሐውልት በሚገኘው ሲኒማ አዳራሽ።
በሸባ ኢንተርተይመንት አዘጋጅነት የቀረበ ሲሆን፣ በቅርቡ በትግራይ ቴሌቪዥን በሳምንት ሦስት ጊዜ ለተመልካች ይደርሳል።
አታኽልቲ ነጋ "ያለ ግንድ ቅርንጫፍ የለም" የሚለውን አባባል በተግባር ያሳየ፣ ለብዙ ወጣት ባለሙያዎች ፈር ቀዳጅ የሆነ የጥበብ መምህር ነው። ይህ አዲስ ስራው የቀድሞውን ጣፋጭ የትግርኛ ድራማ ለዛ ይዞ እንደሚመጣ ጥርጥር የለውም። ሁላችሁም እሁድ በመቐለ በመገኘት ይህንን የጥበብ ጀግና እንድታበረታቱ ጥሪዬን አቀርባለሁ።
(Trailer) ለማየት፦ እዚህ ይጫኑ
ጥበብን በባለቤቱ፣ ታሪክን በፈጣሪው!
ብቸኛ አዘጋጅ
( Exclusive producer ) ሸባ ኢንተርተይመንት
በክብሮም ገ/መስቀል
የዚህን ተከታታይ ድራማ ማስተዋወቂያ (Trailer) ለመመልከት ይህንን ሊንክ ይጠቀሙ፦ https://youtu.be/T6zFaqse6...
#getu #atakltinega #tigrayfilm #wishtindegen #shebaentertainment #tigrinyadrama #ethiopianart #mekelle #insideoutside #አታኽልቲነጋ #መቀሌ #ጥበብ #ትግርኛፊልም #ጌጡተመስገን #getutemesgen
* "ውሽጥን ደገን" ሊመረቅ ነው
#ethiopia | ከሦስት አስርተ ዓመታት በላይ በትግራይ የፊልምና ድራማ ዘርፍ ላይ የማይደበዝዝ አሻራ ያሳረፈው፣ መምህር፣ ደራሲና ተዋናይ አታኽልቲ ነጋ ዳግም ወደ ስክሪን ተመልሷል።
በ"ማሾ" እና "ምትሓታዊ ዓለባ" (ብርሆን ገይፀን) የብዙዎችን ልብ የገዛው ይህ የጥበብ ሰው፣ አሁን ደግሞ "ውሽጥን ደገን" (Inside/Outside) በተሰኘ አዲስ የሲትኮም ድራማ ብቅ ብሏል።
ቀን፦
እሁድ ከሰዓት በኋላ 8፡00 ሰዓት።
ቦታ፦
በመቀለ ሰማዕታት ሐውልት በሚገኘው ሲኒማ አዳራሽ።
በሸባ ኢንተርተይመንት አዘጋጅነት የቀረበ ሲሆን፣ በቅርቡ በትግራይ ቴሌቪዥን በሳምንት ሦስት ጊዜ ለተመልካች ይደርሳል።
አታኽልቲ ነጋ "ያለ ግንድ ቅርንጫፍ የለም" የሚለውን አባባል በተግባር ያሳየ፣ ለብዙ ወጣት ባለሙያዎች ፈር ቀዳጅ የሆነ የጥበብ መምህር ነው። ይህ አዲስ ስራው የቀድሞውን ጣፋጭ የትግርኛ ድራማ ለዛ ይዞ እንደሚመጣ ጥርጥር የለውም። ሁላችሁም እሁድ በመቐለ በመገኘት ይህንን የጥበብ ጀግና እንድታበረታቱ ጥሪዬን አቀርባለሁ።
(Trailer) ለማየት፦ እዚህ ይጫኑ
ጥበብን በባለቤቱ፣ ታሪክን በፈጣሪው!
ብቸኛ አዘጋጅ
( Exclusive producer ) ሸባ ኢንተርተይመንት
በክብሮም ገ/መስቀል
የዚህን ተከታታይ ድራማ ማስተዋወቂያ (Trailer) ለመመልከት ይህንን ሊንክ ይጠቀሙ፦ https://youtu.be/T6zFaqse6...
#getu #atakltinega #tigrayfilm #wishtindegen #shebaentertainment #tigrinyadrama #ethiopianart #mekelle #insideoutside #አታኽልቲነጋ #መቀሌ #ጥበብ #ትግርኛፊልም #ጌጡተመስገን #getutemesgen
2 months ago
የሟች ህፃን ናኦድ አጎት የሞት ቅጣት ተላልፈበት
#ethiopia | ላልተገባ ጥቅም ሲባል ህፃን ናኦድ ተኽላይን በአስቃቂ ጭካኔ የገደሉ አራት ወንጀለኞች ከሞት እስከ 23 ዓመት በሚደርስ ፅኑ እስራት ተቀጡ።
ከአራቱ ወንጀለኞች አንዱ በሌለበት የ25 ዓመት ፅኑ እስራት ተፈርዶበታል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ላለፉት ዘጠኝ ወራት ሲከታተለው የቆየው አሰቃቂ የግድያ ወንጀል የፍርድ ውሳኔ አግኝቷል።
ሟች ህፃን ናኦድ ተኽላይ ሀምሌ 25 ቀን 2017 ዓ.ም በትግራይ ሰሜናዊ ምዕራብ ዞን እንዳስላሰ-ሽረ ከተማ ዙሪያ ነበር አሰቃቂ ግድያ የተፈፀመበት።
ግድያው የተፈጸመው ታግቶ ለማስለቀቂያ 2 ሚሊዮን ብር ከተጠየቀበት በኋላ ነው።
የሟች እናት ወ/ሮ ዮርዳኖስ ጋይም " በልጄ ግድያ ቁጥር አንድ ተጠርጣሪ የሆነው የቅርብ ቤተሰብ በህግ ቁጥጥር ስር ቢሆንም እስከ አሁን የተሰጠው የፍርድ ውሳኔ የለም " በማለት የፍትህ መዘግየቱ እጅግ እንዳሳዘናቸው መግለፃቸውን አስነብበን ነበር።
" የዘገየ ፍትህ እንዳልተሰጠ ይቆጠራል " ሲሉ ነበር የሟች እናት የገለጹት።
ጭካኔ የተሞላበት የግድያ አፈፃፀሙ ከአንድ ዓመት በላይ ሲከታተል የቆየው የሰሜናዊ ምዕራብ ዞን ማእከላዊ ፍርድ ቤት ዛሬ ማክሰኞ መጋቢት 22/2018 ዓ.ም ባዋለው ችሎት በሦስት ወንጀለኞች ላይ የመጨረሻ ውሳኔ አስተላልፏል።
በዚሁ መሰረት ፦
- የሟች ህፃን ናኦድ እናት #ወንድም በሆነው አንደኛ ተከሳሽ ክብሮም ገ/ማርያም የሞት ቅጣት፤
- ከሰተ ደበብና ፀጋይ የተባሉ ተከሳሾች እያንዳንዳቸው የ23 ዓመት ፅኑ እስራት፤
- ወንጀሉን ፈፅሞ የተሰወረው አራተኛ ተከሳሽ ዓንዶም ገ/ሊባኖስ በሌለበት የ25 ዓመታት ፅኑ እስራት እንዲቀጡ ፍርድ ቤት መወሰኑ ተዘግቧል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #rip #deathpenalty #court #tigray #mekelle
#ethiopia | ላልተገባ ጥቅም ሲባል ህፃን ናኦድ ተኽላይን በአስቃቂ ጭካኔ የገደሉ አራት ወንጀለኞች ከሞት እስከ 23 ዓመት በሚደርስ ፅኑ እስራት ተቀጡ።
ከአራቱ ወንጀለኞች አንዱ በሌለበት የ25 ዓመት ፅኑ እስራት ተፈርዶበታል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ላለፉት ዘጠኝ ወራት ሲከታተለው የቆየው አሰቃቂ የግድያ ወንጀል የፍርድ ውሳኔ አግኝቷል።
ሟች ህፃን ናኦድ ተኽላይ ሀምሌ 25 ቀን 2017 ዓ.ም በትግራይ ሰሜናዊ ምዕራብ ዞን እንዳስላሰ-ሽረ ከተማ ዙሪያ ነበር አሰቃቂ ግድያ የተፈፀመበት።
ግድያው የተፈጸመው ታግቶ ለማስለቀቂያ 2 ሚሊዮን ብር ከተጠየቀበት በኋላ ነው።
የሟች እናት ወ/ሮ ዮርዳኖስ ጋይም " በልጄ ግድያ ቁጥር አንድ ተጠርጣሪ የሆነው የቅርብ ቤተሰብ በህግ ቁጥጥር ስር ቢሆንም እስከ አሁን የተሰጠው የፍርድ ውሳኔ የለም " በማለት የፍትህ መዘግየቱ እጅግ እንዳሳዘናቸው መግለፃቸውን አስነብበን ነበር።
" የዘገየ ፍትህ እንዳልተሰጠ ይቆጠራል " ሲሉ ነበር የሟች እናት የገለጹት።
ጭካኔ የተሞላበት የግድያ አፈፃፀሙ ከአንድ ዓመት በላይ ሲከታተል የቆየው የሰሜናዊ ምዕራብ ዞን ማእከላዊ ፍርድ ቤት ዛሬ ማክሰኞ መጋቢት 22/2018 ዓ.ም ባዋለው ችሎት በሦስት ወንጀለኞች ላይ የመጨረሻ ውሳኔ አስተላልፏል።
በዚሁ መሰረት ፦
- የሟች ህፃን ናኦድ እናት #ወንድም በሆነው አንደኛ ተከሳሽ ክብሮም ገ/ማርያም የሞት ቅጣት፤
- ከሰተ ደበብና ፀጋይ የተባሉ ተከሳሾች እያንዳንዳቸው የ23 ዓመት ፅኑ እስራት፤
- ወንጀሉን ፈፅሞ የተሰወረው አራተኛ ተከሳሽ ዓንዶም ገ/ሊባኖስ በሌለበት የ25 ዓመታት ፅኑ እስራት እንዲቀጡ ፍርድ ቤት መወሰኑ ተዘግቧል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #rip #deathpenalty #court #tigray #mekelle
6 months ago
#mekelle
የታጠቁ የትግራይ ኃይሎች ዛሬ ከጥዋት አንስቶ በመቐለ የሚገኘውን የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዚዳንት ፅ/ቤትን ከበው ሰራተኞች እና ተሽከርካሪዎች እንዳይገቡ ፣ በአካባቢው ተሽከርካሪዎች እንዳይንቀሳቀሱ አግደው እንደነበር ቲክቫህ ኢትዮጵያ ለማወቅ ችሏል።
ብሬን ፣ ክላሽ የታጠቁት ኃይሎች ከጥዋት አንስተው ወደ ፅ/ቤቱ የሚወስደውን መንገድ በመዝጋት ፣ ዙሪያውን በመክበብ፣ የትራንስፖርት እንቅስቃሴ እንዳይኖር አድርገው አርፍደዋል።
ሰራተኞችና ተሽከርካሪዎች እንዳይገቡ ከውስጥም ሰው እንዳይወጣ፣ ወደ ስፍራው ሰው እንዳይጠጋ በመከልከላቸው የፅ/ቤቱ ሰራተኞች ውጭ ላይ ቆመው እንደነበር ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከአይን እማኞች ተረድቷል።
ቃላቸውን የሰጡን ነዋሪዎች እንቅስቃሴው የነበረው የፕሬዜዳንት ፅ/ቤት አካባቢ ብቻ እንደነበር ከዛ ውጭ ከተማው ሙሉ ሰላም እንደሆነ ገልጸዋል።
ከግማሽ ሰዓት በፊት ታጣቂዎቹ አካባቢውን ክፍት ማድረጋቸው፣ ሰራተኞችም ወደ ስራ መግባታቸው ፣ መንገዶች ለትራንስፖርት እንቅስቃሴ ክፍት መደረጋቸውን ለማወቅ ችለናል።
የታጣቂዎቹ እንቅስቃሴ ከዚህ ቀደም ከነበረው የደመወዝ እና ሌሎች ተያያዥ ጥያቄዎች ጋር የተገናኘ ነው።
ከሰዓት በኃላ የሚሰጥ መግለጫ ካለ ተከታትለን እናቀርባለን።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
tikvahethiopia
የታጠቁ የትግራይ ኃይሎች ዛሬ ከጥዋት አንስቶ በመቐለ የሚገኘውን የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዚዳንት ፅ/ቤትን ከበው ሰራተኞች እና ተሽከርካሪዎች እንዳይገቡ ፣ በአካባቢው ተሽከርካሪዎች እንዳይንቀሳቀሱ አግደው እንደነበር ቲክቫህ ኢትዮጵያ ለማወቅ ችሏል።
ብሬን ፣ ክላሽ የታጠቁት ኃይሎች ከጥዋት አንስተው ወደ ፅ/ቤቱ የሚወስደውን መንገድ በመዝጋት ፣ ዙሪያውን በመክበብ፣ የትራንስፖርት እንቅስቃሴ እንዳይኖር አድርገው አርፍደዋል።
ሰራተኞችና ተሽከርካሪዎች እንዳይገቡ ከውስጥም ሰው እንዳይወጣ፣ ወደ ስፍራው ሰው እንዳይጠጋ በመከልከላቸው የፅ/ቤቱ ሰራተኞች ውጭ ላይ ቆመው እንደነበር ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከአይን እማኞች ተረድቷል።
ቃላቸውን የሰጡን ነዋሪዎች እንቅስቃሴው የነበረው የፕሬዜዳንት ፅ/ቤት አካባቢ ብቻ እንደነበር ከዛ ውጭ ከተማው ሙሉ ሰላም እንደሆነ ገልጸዋል።
ከግማሽ ሰዓት በፊት ታጣቂዎቹ አካባቢውን ክፍት ማድረጋቸው፣ ሰራተኞችም ወደ ስራ መግባታቸው ፣ መንገዶች ለትራንስፖርት እንቅስቃሴ ክፍት መደረጋቸውን ለማወቅ ችለናል።
የታጣቂዎቹ እንቅስቃሴ ከዚህ ቀደም ከነበረው የደመወዝ እና ሌሎች ተያያዥ ጥያቄዎች ጋር የተገናኘ ነው።
ከሰዓት በኃላ የሚሰጥ መግለጫ ካለ ተከታትለን እናቀርባለን።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
tikvahethiopia
11 months ago
📌" እያንዳንድሽ ትመጫታለሽ”
የፌስቡኩ ሰፈር አድማቂ የመቐለ
ታላቁ ምሁርን እንሰናበተው
ፕሮፌሰር Hassen Mohammed ትቶን ሄደ
#ethiopia | ሁሌም ነገሮችን ቀለል አርጎ ሲያይ በህመሙ እንኳን ሲቀልድ ነው የማውቀው። ከፌስቡክ መራቄን ያወቅኩት ሀሰን ከአንድ ወር በፊት ኩላሊቱ ፌል አድርጎ እርዳታ ጠይቆ እንደነበረ አሁን ካለፈ በኋላ ስሰማ ነው 😭
ሀወይ የመቀሌው ምሁር ደህና ሁን አቦ👋😭
የዛሬ ሁለት አመት በፃፈው ፖስት ልጨርስ
" እያንዳንድሽ ትመጫታለሽ
በፎቶ የምታዩት ኮልፌ የመቃብር ስፍራ ነው። እንዴት "አድጓል"? ከብዙ አመታት በኋላ ብመጣ ምን አክሏል?! ከኔ ብቻ ነፍ ሰው ወስዷል። ከአያቶቼ ጀምሮ፣ የልቤ ክፋይ እናት አባት፣ አጎት አክስት እንዲሁም ብዙ ሌሎች የምወዳቸው ... ሁሉ በዚህ በኩል ነው የሄዱት። አላህ ይራህማቸው! ትናንት እና ዛሬም ተጨማምሯል። መንሱር ወንድማችንን አላህ ይራህመው! የመቐለው ወዳጅና የስራ ባለደረባችን ዶር ያሲንንም አላህ ይራህመው! መቐለ ሆነ አዲሳባ ለአዝራኤል ሁሉም ኮልፌ ነው። በክራንች ስለማያስገባ ከሩቅ ሆኜ ሁሉንም ዘየርኩ። የራሴን ፊውቸርም በዚያው። በምልክት "ደውላለሁ" አልኩት 😀 ሳበሳ
ይቺ ለረመዳኑም ለህማማቱም ትጠቅማለች ብዬ አሰብኩ። መተናነስ ነውና አላማቸው። ኃይል አለኝ ለምትል፣ እንጣጥ እንጣጥ የምትል ሁላ ትመጣታለህ! ወደ ትቢያ ትቀላቀላለህም። እንደማለት ነገር።
ድሮ ያየሁትና የረሳሁት መፅሄት ላይ የሆነ አገር ለአንድ ከተማ ከንቲባ ጥያቄ ቀረበ። የሆነ ታዋቂ ቀራፂ የከተማዋ ክፍት ቦታዎች እንዲሰጡት ጠየቀ። አላማው የመቃብር ሐውልት ቅርፆችን ለመትከል ነበር። ሰዎች ለህይወት ትኩረትም ትርጉምም አይሰጡም፣ በደመነብስ ይራወጣሉ። ቢሰጡም እንኳን ከፍተኛ የዝንጋታ ችግር አለባቸው። የዚህ ቀራፂ አላማ ታድያ ስናልፍ ስናገድም፣ ስንንቀዋለል ስንሮጥ አይተን ደንገጥ እንድንል ነው። እንድናስታውስ ነው። ቅድሚያ ለሚገባው ቅድሚያ እንድንሰጥ ነው። ጥብርር ስንል፣ ስንደነፋ፣ ያዙኝ ልቀቁኝ ስንል ድንገት ቀና ብለን አይተን "what's the point?!" እንድንል። "ምን ዋጋ አለው?"፣ "ምን ትርጉም አለው?" እንድንል እና ወደ መልካምነታችን እንድንመለስ ነው። የኔም አላማ ይሄው ነው። ሰናይ ምሽት!" #tesfag
***
ሀሰኖ! Hassen Mohammed ወዱ መምህራችን!
የ Mekelle University School of Law ትዝታችን እና ታሪካችን አንዱ አንተ ነበርክ። ቅንነትህን ፍትሐዊነትህን አሰላሳይነትህን እና የቋንቋ ችሎታህን ፉገራና ጨዋታህን (ሳበሳ) አንረሳውም።
በሰላም እረፍ!
ነፍስ ይማር።
ተማሪህ
የፌስቡኩ ሰፈር አድማቂ የመቐለ
ታላቁ ምሁርን እንሰናበተው
ፕሮፌሰር Hassen Mohammed ትቶን ሄደ
#ethiopia | ሁሌም ነገሮችን ቀለል አርጎ ሲያይ በህመሙ እንኳን ሲቀልድ ነው የማውቀው። ከፌስቡክ መራቄን ያወቅኩት ሀሰን ከአንድ ወር በፊት ኩላሊቱ ፌል አድርጎ እርዳታ ጠይቆ እንደነበረ አሁን ካለፈ በኋላ ስሰማ ነው 😭
ሀወይ የመቀሌው ምሁር ደህና ሁን አቦ👋😭
የዛሬ ሁለት አመት በፃፈው ፖስት ልጨርስ
" እያንዳንድሽ ትመጫታለሽ
በፎቶ የምታዩት ኮልፌ የመቃብር ስፍራ ነው። እንዴት "አድጓል"? ከብዙ አመታት በኋላ ብመጣ ምን አክሏል?! ከኔ ብቻ ነፍ ሰው ወስዷል። ከአያቶቼ ጀምሮ፣ የልቤ ክፋይ እናት አባት፣ አጎት አክስት እንዲሁም ብዙ ሌሎች የምወዳቸው ... ሁሉ በዚህ በኩል ነው የሄዱት። አላህ ይራህማቸው! ትናንት እና ዛሬም ተጨማምሯል። መንሱር ወንድማችንን አላህ ይራህመው! የመቐለው ወዳጅና የስራ ባለደረባችን ዶር ያሲንንም አላህ ይራህመው! መቐለ ሆነ አዲሳባ ለአዝራኤል ሁሉም ኮልፌ ነው። በክራንች ስለማያስገባ ከሩቅ ሆኜ ሁሉንም ዘየርኩ። የራሴን ፊውቸርም በዚያው። በምልክት "ደውላለሁ" አልኩት 😀 ሳበሳ
ይቺ ለረመዳኑም ለህማማቱም ትጠቅማለች ብዬ አሰብኩ። መተናነስ ነውና አላማቸው። ኃይል አለኝ ለምትል፣ እንጣጥ እንጣጥ የምትል ሁላ ትመጣታለህ! ወደ ትቢያ ትቀላቀላለህም። እንደማለት ነገር።
ድሮ ያየሁትና የረሳሁት መፅሄት ላይ የሆነ አገር ለአንድ ከተማ ከንቲባ ጥያቄ ቀረበ። የሆነ ታዋቂ ቀራፂ የከተማዋ ክፍት ቦታዎች እንዲሰጡት ጠየቀ። አላማው የመቃብር ሐውልት ቅርፆችን ለመትከል ነበር። ሰዎች ለህይወት ትኩረትም ትርጉምም አይሰጡም፣ በደመነብስ ይራወጣሉ። ቢሰጡም እንኳን ከፍተኛ የዝንጋታ ችግር አለባቸው። የዚህ ቀራፂ አላማ ታድያ ስናልፍ ስናገድም፣ ስንንቀዋለል ስንሮጥ አይተን ደንገጥ እንድንል ነው። እንድናስታውስ ነው። ቅድሚያ ለሚገባው ቅድሚያ እንድንሰጥ ነው። ጥብርር ስንል፣ ስንደነፋ፣ ያዙኝ ልቀቁኝ ስንል ድንገት ቀና ብለን አይተን "what's the point?!" እንድንል። "ምን ዋጋ አለው?"፣ "ምን ትርጉም አለው?" እንድንል እና ወደ መልካምነታችን እንድንመለስ ነው። የኔም አላማ ይሄው ነው። ሰናይ ምሽት!" #tesfag
***
ሀሰኖ! Hassen Mohammed ወዱ መምህራችን!
የ Mekelle University School of Law ትዝታችን እና ታሪካችን አንዱ አንተ ነበርክ። ቅንነትህን ፍትሐዊነትህን አሰላሳይነትህን እና የቋንቋ ችሎታህን ፉገራና ጨዋታህን (ሳበሳ) አንረሳውም።
በሰላም እረፍ!
ነፍስ ይማር።
ተማሪህ
Sponsored by
Surafel