21 hours ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) በአዲስ አበባ የተጠራው የሱዳን ፖለቲካ ሀይሎች ስብሰባ ውዝግብ ፈጠረ፡፡ በአዲስ አበባ ከተማ ከዛሬ አንስቶ ለሚቀጥሉት ቀናት የሚካሄደው የሱዳን ፖለቲካ ሀይሎች ውይይት ከጅምሩ ውዝግብ ተፈጥሮበታል፡፡ ስብሰባው የተጠራው አምስትዮሽ ሀይሎች ማለትም በአፍሪካ ህብረት፣ በኢጋድ፣ በተመድ፣ በአውሮፓ ህብረትና በአረብ ሊግ አማካኝነት ነው፡፡
የስብሰባው ዋነኛ አላማም ባለፈው ወር በበርሊን በተከናወነው 3ተኛው የሱዳን አለም አቀፍ ጉባኤ ላይ ያልተሳተፉ የፖለቲካ ሀይሎችን አገናኝቶ እንዲወያዩ ማድረግ ነው፡፡ በስብሰባው ላይ በርካታ የፖለቲካ ፓርቲዎች እንደሚሳተፉ አስቀድመው ገልፀው የነበረ ቢሆንም በመጨረሻ ሰአት ግን ራሳቸውን ማግለላቸውን የገለፁ ፓርቲዎች እንዳሉ ሱዳን ትሪቢዩን ዘግቧል፡፡ በተለይም ‹‹ሶሙድ›› በሚል የሚጠራው የተለያዩ ፖለቲካ ፓርቲዎችን ያቀፈው ግንባር ክፍፍል መፍጠሩን አስረድቷል፡፡
በቀድሞው የሱዳን ጠቅላይ ሚኒስትር አብደላ ሀምዶክ የሚመራው ሶሙድ ውስጥ ከተጠቃለሉት ፓርቲዎች መካከል የተወሰኑት አዲስ አበባ ሲገቡ የተወሰኑት ደግሞ መቅረታቸውን ዘገባው አስታውቋል፡፡ በዚህ ስብሰባ ላይ የመሀመድ ዳጋሎ ፈጥኖ ደራሽ ሀይል አጋር የሆኑ ፓርቲዎች እየተሳተፉ መሆኑን የጠቀሰው ዘገባው በሌተና ጄኔራል አልብሩሀን የሚመራው መንግስት ጥሪ ቢደርሰውም ለመሳተፍ ፈቃደኛ ሳይሆን መቅረቱን ገልጿል፡፡ አምስቱ ቀጣናዊና አለም አቀፍ ድርጅቶች ያዘጋጁት ይህ ስብሰባ በሁለት የተከፈለ ሲሆን ዛሬ የተጀመረው አንደኛው ክፍል ነው፡፡ በቀጣይነት ማለትም ከጁላይ 8 እስከ 9 ሌላ የሱዳን ፖለቲካ ሀይሎችን ያሳተፈ ስብሰባ እንደሚደረግም ዘገባው አስታውቋል፡፡
የስብሰባው ዋነኛ አላማም ባለፈው ወር በበርሊን በተከናወነው 3ተኛው የሱዳን አለም አቀፍ ጉባኤ ላይ ያልተሳተፉ የፖለቲካ ሀይሎችን አገናኝቶ እንዲወያዩ ማድረግ ነው፡፡ በስብሰባው ላይ በርካታ የፖለቲካ ፓርቲዎች እንደሚሳተፉ አስቀድመው ገልፀው የነበረ ቢሆንም በመጨረሻ ሰአት ግን ራሳቸውን ማግለላቸውን የገለፁ ፓርቲዎች እንዳሉ ሱዳን ትሪቢዩን ዘግቧል፡፡ በተለይም ‹‹ሶሙድ›› በሚል የሚጠራው የተለያዩ ፖለቲካ ፓርቲዎችን ያቀፈው ግንባር ክፍፍል መፍጠሩን አስረድቷል፡፡
በቀድሞው የሱዳን ጠቅላይ ሚኒስትር አብደላ ሀምዶክ የሚመራው ሶሙድ ውስጥ ከተጠቃለሉት ፓርቲዎች መካከል የተወሰኑት አዲስ አበባ ሲገቡ የተወሰኑት ደግሞ መቅረታቸውን ዘገባው አስታውቋል፡፡ በዚህ ስብሰባ ላይ የመሀመድ ዳጋሎ ፈጥኖ ደራሽ ሀይል አጋር የሆኑ ፓርቲዎች እየተሳተፉ መሆኑን የጠቀሰው ዘገባው በሌተና ጄኔራል አልብሩሀን የሚመራው መንግስት ጥሪ ቢደርሰውም ለመሳተፍ ፈቃደኛ ሳይሆን መቅረቱን ገልጿል፡፡ አምስቱ ቀጣናዊና አለም አቀፍ ድርጅቶች ያዘጋጁት ይህ ስብሰባ በሁለት የተከፈለ ሲሆን ዛሬ የተጀመረው አንደኛው ክፍል ነው፡፡ በቀጣይነት ማለትም ከጁላይ 8 እስከ 9 ሌላ የሱዳን ፖለቲካ ሀይሎችን ያሳተፈ ስብሰባ እንደሚደረግም ዘገባው አስታውቋል፡፡
2 days ago
የግብፅን የኢትዮጵያ የባህር በር ጥረት ማደናቀፍ እንቅስቃሴ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ኮነነ
#ethiopia | የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ግብፅ ሀገሪቱ የወደብ ባለቤት እንዳትሆን እያደረገች ያለውን ዲፕሎማሲያዊ ጫና እና የእንቅፋት ፈጠራ ስትራቴጂ አጥብቆ ተቃውሟል።
የቀይ ባህር ጉዳይ የሚመለከተው የባህር ዳርቻ ያላቸውን ሀገራት ብቻ ነው በማለት በግብፅ በኩል የሚሰነዘረውን አቋም የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነቢያት ጌታቸው ፍጹም ተቀባይነት የሌለው ሲሉ አጣጥለውታል።
በተጨማሪም ግብፅ በቅርቡ ከኤርትራ፣ ሶማሊያ እና ሱዳን ጋር የመሰረተችው ወታደራዊ እንዲሁም ኢኮኖሚያዊ ትብብር ኢትዮጵያን በዲፕሎማሲው መድረክ የማግለልና የመክበብ ስልት አካል ተደርጎ ተወስዷል።
ይህ አዲስ ውጥረት ከታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ድርድር አለመግባባት ጋር የተያያዘ ቢሆንም፣ ኢትዮጵያ ግን የወደብ ባለቤት ለመሆን የጀመረችውን ዲፕሎማሲያዊ ጥረት በቁርጠኝነት እንደምትቀጥል አስታውቃለች።
በተለይም ከሶማሊላንድ ጋር የተፈረመውን የመግባቢያ ሰነድ ጨምሮ፣ ሀገሪቱ ያላትን የባህር በር የማግኘት ህጋዊ ፍላጎት በማናቸውም ውጫዊ ጫና ሳትበገር በሰላማዊ መንገድ እንደምታስፈጽም ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ በድጋሚ አረጋግጧል።
#ግብፅ #የባህርበር #የቀይባህር #የህዳሴግድብ #ዲፕሎማሲ #የአፍሪካቀንድ #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ግብፅ ሀገሪቱ የወደብ ባለቤት እንዳትሆን እያደረገች ያለውን ዲፕሎማሲያዊ ጫና እና የእንቅፋት ፈጠራ ስትራቴጂ አጥብቆ ተቃውሟል።
የቀይ ባህር ጉዳይ የሚመለከተው የባህር ዳርቻ ያላቸውን ሀገራት ብቻ ነው በማለት በግብፅ በኩል የሚሰነዘረውን አቋም የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነቢያት ጌታቸው ፍጹም ተቀባይነት የሌለው ሲሉ አጣጥለውታል።
በተጨማሪም ግብፅ በቅርቡ ከኤርትራ፣ ሶማሊያ እና ሱዳን ጋር የመሰረተችው ወታደራዊ እንዲሁም ኢኮኖሚያዊ ትብብር ኢትዮጵያን በዲፕሎማሲው መድረክ የማግለልና የመክበብ ስልት አካል ተደርጎ ተወስዷል።
ይህ አዲስ ውጥረት ከታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ድርድር አለመግባባት ጋር የተያያዘ ቢሆንም፣ ኢትዮጵያ ግን የወደብ ባለቤት ለመሆን የጀመረችውን ዲፕሎማሲያዊ ጥረት በቁርጠኝነት እንደምትቀጥል አስታውቃለች።
በተለይም ከሶማሊላንድ ጋር የተፈረመውን የመግባቢያ ሰነድ ጨምሮ፣ ሀገሪቱ ያላትን የባህር በር የማግኘት ህጋዊ ፍላጎት በማናቸውም ውጫዊ ጫና ሳትበገር በሰላማዊ መንገድ እንደምታስፈጽም ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ በድጋሚ አረጋግጧል።
#ግብፅ #የባህርበር #የቀይባህር #የህዳሴግድብ #ዲፕሎማሲ #የአፍሪካቀንድ #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
2 days ago
⚡ "የጽምዶ ጥምረት" በርካታ የኢትዮጵያ ተቃዋሚ ቡድኖችን እያካተተ መሆኑ ተገለጠ
በኤርትራ እና ህወሃት መካከል የተጀመረውና "ጽምዶ" (Ximdo) በመባል የሚታወቀው አዲሱ የፖለቲካ ትስስር፣ አሁን ላይ በርካታ የኢትዮጵያ የታጠቁና የፖለቲካ ተቃዋሚ ቡድኖችን ወደማካተት እየሰፋ መሄዱን አፍሪካ ኢንተለጀንስ ዘግቧል።
📌 የአዲስ አበባውን ማዕከላዊ መንግስት የሚቃወሙት የህወሃት/ትግራይ መከላከያ ኃይል አመራሮች፣ በቅርቡ በሱዳን የወደብ ከተማ ፖርት ሱዳን ከተደረጉ የኤርትራ ከፍተኛ ባለስልጣናት እና ከሱዳን ጦር ኃይል ተወካዮች ጋር ስብሰባ ማድረጋቸው ተረጋግጧል።
ይህ በኤርትራ መንግስት አስተባባሪነት እየተመራ ያለው ጥምረት የህወሃትን "የአሮጌው ጎራ ጨምሮ፣ እንደ ፋኖ ያሉ፣ የኦብነግ የተገነጠሉ ክንፎችን እና ሌሎች ታዋቂ የፖለቲካ ተቃዋሚዎችን በአንድ ጥላ ስር ለማሰባሰብ እየሰራ እንደሆነ የደህንነት ምንጮች ጠቁመዋል።
የሰሜኑ ጦርነት ወቅት ኤርትራ እና ህወሃት እርስ በእርስ የገጠሙ ደመኛ ጠላቶች የነበሩ ቢሆንም፣ አሁን ላይ ግን "የጠላቴ ጠላት ወዳጄ ነው" በሚለው መርህ የአዲስ አበባውን መንግስት ለመጫንና የራሳቸውን የፖለቲካ ህልውና ለማስጠበቅ ስልታዊ ህብረት ፈጥረዋል።ይህ አዲስ የሀይሎች መሸጋሸግ በኢትዮጵያ፣ በኤርትራ እና በሱዳን መካከል ያለውን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ይበልጥ እያሻከረው ሲሆን፣ ቀጠናዊ ቀውስ ሊያስከትል ይችላል የሚል ስጋት ፈጥሯል።
Seledadotio
Seledadotio
በኤርትራ እና ህወሃት መካከል የተጀመረውና "ጽምዶ" (Ximdo) በመባል የሚታወቀው አዲሱ የፖለቲካ ትስስር፣ አሁን ላይ በርካታ የኢትዮጵያ የታጠቁና የፖለቲካ ተቃዋሚ ቡድኖችን ወደማካተት እየሰፋ መሄዱን አፍሪካ ኢንተለጀንስ ዘግቧል።
📌 የአዲስ አበባውን ማዕከላዊ መንግስት የሚቃወሙት የህወሃት/ትግራይ መከላከያ ኃይል አመራሮች፣ በቅርቡ በሱዳን የወደብ ከተማ ፖርት ሱዳን ከተደረጉ የኤርትራ ከፍተኛ ባለስልጣናት እና ከሱዳን ጦር ኃይል ተወካዮች ጋር ስብሰባ ማድረጋቸው ተረጋግጧል።
ይህ በኤርትራ መንግስት አስተባባሪነት እየተመራ ያለው ጥምረት የህወሃትን "የአሮጌው ጎራ ጨምሮ፣ እንደ ፋኖ ያሉ፣ የኦብነግ የተገነጠሉ ክንፎችን እና ሌሎች ታዋቂ የፖለቲካ ተቃዋሚዎችን በአንድ ጥላ ስር ለማሰባሰብ እየሰራ እንደሆነ የደህንነት ምንጮች ጠቁመዋል።
የሰሜኑ ጦርነት ወቅት ኤርትራ እና ህወሃት እርስ በእርስ የገጠሙ ደመኛ ጠላቶች የነበሩ ቢሆንም፣ አሁን ላይ ግን "የጠላቴ ጠላት ወዳጄ ነው" በሚለው መርህ የአዲስ አበባውን መንግስት ለመጫንና የራሳቸውን የፖለቲካ ህልውና ለማስጠበቅ ስልታዊ ህብረት ፈጥረዋል።ይህ አዲስ የሀይሎች መሸጋሸግ በኢትዮጵያ፣ በኤርትራ እና በሱዳን መካከል ያለውን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ይበልጥ እያሻከረው ሲሆን፣ ቀጠናዊ ቀውስ ሊያስከትል ይችላል የሚል ስጋት ፈጥሯል።
Seledadotio
Seledadotio
2 days ago
⚡ "ግብፅ ወደ ባህር በር እንዳንደርስ እያገደችን ነው" — ኢትዮጵያ
ኢትዮጵያ የባህር በር ለማግኘት የምታደርገውን ጥረት ግብፅ ለማደናቀፍ እየሞከረች ነው ስትል በይፋ ከሰሰች። የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነቢያት ጌታቸው፣ የግብፅን አካሄድ "ተቀባይነት የሌለው" ሲሉ ኮንነዋል።
📌 ግብፅ በቅርቡ ከኤርትራ፣ ከሶማሊያ እና ከሱዳን ጋር ወታደራዊና ኢኮኖሚያዊ ስምምነቶችን በማድረግ ኢትዮጵያን የመክበብ ስትራቴጂ እየተከተለች እንደሆነ ይነገራል። የግብፅ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር "የቀይ ባህር ጉዳይ የሚመለከተው የባህር ጠረፍ ያላቸውን ሀገራት ብቻ ነው" ማለታቸው፣ ኢትዮጵያን በዲፕሎማሲ የማግለል ሙከራ ተደርጎ ተወስዷል።
አለመግባባቱ ከህዳሴው ግድብ ውጥረት ጋር የተያያዘ ቢሆንም፣ ኢትዮጵያ ከሶማሊላንድ ጋር የጀመረችውን ጨምሮ የባህር በር ባለቤት የመሆን ፍላጎቷን በሰላማዊ መንገድ እንደምትቀጥል አስታውቃለች
Seledadotio
Seledadotio
ኢትዮጵያ የባህር በር ለማግኘት የምታደርገውን ጥረት ግብፅ ለማደናቀፍ እየሞከረች ነው ስትል በይፋ ከሰሰች። የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነቢያት ጌታቸው፣ የግብፅን አካሄድ "ተቀባይነት የሌለው" ሲሉ ኮንነዋል።
📌 ግብፅ በቅርቡ ከኤርትራ፣ ከሶማሊያ እና ከሱዳን ጋር ወታደራዊና ኢኮኖሚያዊ ስምምነቶችን በማድረግ ኢትዮጵያን የመክበብ ስትራቴጂ እየተከተለች እንደሆነ ይነገራል። የግብፅ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር "የቀይ ባህር ጉዳይ የሚመለከተው የባህር ጠረፍ ያላቸውን ሀገራት ብቻ ነው" ማለታቸው፣ ኢትዮጵያን በዲፕሎማሲ የማግለል ሙከራ ተደርጎ ተወስዷል።
አለመግባባቱ ከህዳሴው ግድብ ውጥረት ጋር የተያያዘ ቢሆንም፣ ኢትዮጵያ ከሶማሊላንድ ጋር የጀመረችውን ጨምሮ የባህር በር ባለቤት የመሆን ፍላጎቷን በሰላማዊ መንገድ እንደምትቀጥል አስታውቃለች
Seledadotio
Seledadotio
2 days ago
የህዳሴ ግድብና የቀይ ባህር ዲፕሎማሲ፡ የኢትዮጵያ አዲስ ጂኦፖለቲካዊ ምዕራፍ
#ethiopia | በ21ኛው ክፍለ ዘመን የአገራት ኃይል የሚለካው በወታደራዊ አቅም ብቻ ሳይሆን የኢኮኖሚ፣ የኢነርጂ፣ የውሃ እና የጂኦፖለቲካ ተጽዕኖ በመፍጠር ጭምር ነው።
በዚህ መሠረት ኢትዮጵያ ባለፉት አስርት ዓመታት ውስጥ በሁለት ታላላቅ ብሔራዊ አጀንዳዎች ዙሪያ የተለየ የዲፕሎማሲ ጉዞ አድርጋለች።
እነዚህም የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ እና የቀይ ባህር ተደራሽነት ጉዳይ ናቸው።
ሁለቱም ጉዳዮች ከኢኮኖሚ ጥቅም ባሻገር የአገሪቱን የህልውና ጥያቄ፣ የቀጣናዊ ተጽዕኖ ፈጣሪነት እና የወደፊት የልማት አቅጣጫ የሚወስኑ ናቸው።
በእነዚህ መስኮች የተመዘገቡ ዲፕሎማሲያዊ ስኬቶችም ኢትዮጵያ በአፍሪካ ቀንድ እና በምሥራቅ አፍሪካ እየተጠናከረ የመጣ የኃይል ማዕከል መሆኗን አመላክተዋል።
የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ከመጀመሪያው ቀን ጀምሮ ከፍተኛ ዓለም አቀፍ ትኩረት የሳበ ፕሮጀክት ነበር።
በተለይም የዓባይ ውሃ አጠቃቀምን በተመለከተ በታሪክ የተፈጠሩ የፖለቲካ እና የጂኦፖለቲካ አለመግባባቶች ግድቡን ከቀላል የልማት ፕሮጀክት ወደ የዲፕሎማሲ ፈተና ቀይረውት ነበር።
ሆኖም ኢትዮጵያ “ፍትሐዊና ምክንያታዊ የውሃ አጠቃቀም” እንዲሁም “በሌሎች ላይ ጉልህ ጉዳት አለማድረስ” በሚሉ ዓለም አቀፍ መርሆዎች ላይ ተመስርታ የተከተለችው የዲፕሎማሲ መንገድ ትልቅ ውጤቶችን አስመዝግቧል።
ከተመዘገቡት ታላላቅ ድሎች አንዱ የግድቡ ጉዳይ በአፍሪካ ሕብረት ማዕቀፍ እንዲመራ ማድረግ ነው።
ጉዳዩን ወደ ዓለም አቀፍ የፖለቲካ መድረኮች በመውሰድ ጫና ለመፍጠር የተደረጉ ጥረቶች ቢኖሩም፣ ኢትዮጵያ የአፍሪካ ችግሮች በአፍሪካውያን መፍትሔ ሊያገኙ ይገባል የሚለውን መርህ በተግባር አስከብራለች።
ይህ የዲፕሎማሲ ድል ለኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ለመላው አፍሪካ የተቋማዊ ነጻነት እና የአህጉራዊ ትብብር ማሳያ ሆኗል።
ሌላው ታላቅ ስኬት የግድቡ ግንባታ በውጭ ጫናዎች ሳይቆም እስከ መጨረሻው የውሃ ሙሌት መድረሱ ነው።
በሕዝብ ገንዘብና በብሔራዊ አንድነት የተገነባው ግድብ የኢትዮጵያን የራስ አቅም እና የውጭ ጫናን የመቋቋም ችሎታ አሳይቷል።
ዛሬ ግድቡ የኤሌክትሪክ ኃይል በማመንጨት ለአጎራባች አገራት ለሚደረገው የኃይል ሽያጭ መሠረት ሆኗል። ይህም ግድቡ የግጭት ምንጭ ሳይሆን የቀጣናዊ ትስስርና የጋራ ልማት መሣሪያ መሆኑን በተግባር አረጋግጧል።
የህዳሴ ግድብ ኢትዮጵያን ከተራ የኤሌክትሪክ አምራች ወደ የቀጣናው የኢነርጂ ማዕከል እየቀየራት ነው። ለጅቡቲ፣ ለኬንያ፣ ለሱዳን እና ለሌሎች አገራት የኃይል አቅርቦት መስፋፋቱ የኢኮኖሚ ትስስርን ከማጠናከሩም በላይ የፖለቲካ መተማመንን እየፈጠረ ነው።
ኢትዮጵያ ከ120 ሚሊዮን በላይ ሕዝብ ያላትና ፈጣን የኢኮኖሚ እድገት እያሳየች ያለች አገር ብትሆንም፣ የባሕር በር አልባ መሆኗ ለንግድ፣ ለኢኮኖሚ እና ለብሔራዊ ደኅንነት ከፍተኛ ፈተና ሆኖ ቆይቷል።
በቅርብ ዓመታት ግን ኢትዮጵያ የባሕር በር ጥያቄዋን ከታሪካዊ ቅሬታ ወደ ስትራቴጂካዊ ዲፕሎማሲ ቀይራለች።
ከሶማሊላንድ ጋር የተፈረመው የመግባቢያ ሰነድ (MoU) በዚህ ረገድ ታሪካዊ እርምጃ ተብሎ ይታያል። ይህ እርምጃ ኢትዮጵያ የባሕር በር ፍላጎቷን በሰላማዊ እና በዲፕሎማሲያዊ መንገድ ለማሳካት ያላትን ቁርጠኝነት አሳይቷል።
ይህ የዲፕሎማሲ አቅጣጫ ኢትዮጵያ ከአንድ ወደብ ብቻ ጥገኛ የመሆን አደጋን ለመቀነስና የንግድ ወጪዋን ለመቆጣጠር የሚያስችል አዲስ የጂኦኢኮኖሚ አስተሳሰብ እንዳላት አሳይቷል።
ቀይ ባህር ከዓለም አቀፍ የንግድ መስመሮች አንዱ እንደመሆኑ መጠን በዚህ አካባቢ የሚፈጠሩ የደኅንነት ችግሮች በቀጥታ ኢትዮጵያን ይነካሉ።
በመሆኑም ኢትዮጵያ በቀይ ባህር ጉዳይ ተመልካች ሳይሆን ንቁ ባለድርሻ መሆን እንዳለባት በዲፕሎማሲ መድረኮች ላይ በግልጽ ማስቀመጥ ችላለች። ይህም የአገሪቱን የጂኦፖለቲካ ተጽዕኖ እያሳደገ ነው።
የህዳሴ ግድብና የቀይ ባህር ዲፕሎማሲ በተለያዩ ጉዳዮች ዙሪያ ቢመስሉም፣ የጋራ ዓላማ አላቸው። ይህም ኢትዮጵያን በኢኮኖሚ፣ በኢነርጂ እና በጂኦፖለቲካ የቀጣናው የኃይል ማዕከል ማድረግ ነው።
የህዳሴ ግድብ የኢነርጂ ተጽዕኖን ሲፈጥር፣ የቀይ ባህር ዲፕሎማሲ ደግሞ የንግድና የስትራቴጂካዊ ተደራሽነትን ያጠናክራል። ሁለቱም ተደጋጋፊ ሲሆኑ የኢትዮጵያን የወደፊት ኢኮኖሚ እና የፖለቲካ ኃይል ለመገንባት ወሳኝ ሚና አላቸው።
በህዳሴ ግድብና በቀይ ባህር ጉዳዮች ዙሪያ የታዩት የዲፕሎማሲ ስኬቶች ኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅሞቿን በውይይት፣ በጽናት እና በስትራቴጂካዊ አመራር ማስከበር እንደምትችል አረጋግጠዋል።
ይሁን እንጂ እነዚህ ድሎች ዘላቂ ውጤት እንዲያመጡ የውስጥ አንድነትን ማጠናከር፣ ከጎረቤት አገራት ጋር በጋራ ተጠቃሚነት ላይ የተመሠረተ ግንኙነት መገንባት እና የሰላም ዲፕሎማሲን ማስቀጠል አስፈላጊ ነው።
የህዳሴ ግድብ የኢነርጂ ነፃነትን ሲያመጣ፣ የቀይ ባህር ዲፕሎማሲ ደግሞ የኢትዮጵያን የጂኦፖለቲካ ተደራሽነት ያሰፋል። ሁለቱም ተደምረው ኢትዮጵያን በአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ ተጽዕኖ ፈጣሪ አገር ወደማድረግ እየመሯት ነው።
ውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር
#ethiopia | በ21ኛው ክፍለ ዘመን የአገራት ኃይል የሚለካው በወታደራዊ አቅም ብቻ ሳይሆን የኢኮኖሚ፣ የኢነርጂ፣ የውሃ እና የጂኦፖለቲካ ተጽዕኖ በመፍጠር ጭምር ነው።
በዚህ መሠረት ኢትዮጵያ ባለፉት አስርት ዓመታት ውስጥ በሁለት ታላላቅ ብሔራዊ አጀንዳዎች ዙሪያ የተለየ የዲፕሎማሲ ጉዞ አድርጋለች።
እነዚህም የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ እና የቀይ ባህር ተደራሽነት ጉዳይ ናቸው።
ሁለቱም ጉዳዮች ከኢኮኖሚ ጥቅም ባሻገር የአገሪቱን የህልውና ጥያቄ፣ የቀጣናዊ ተጽዕኖ ፈጣሪነት እና የወደፊት የልማት አቅጣጫ የሚወስኑ ናቸው።
በእነዚህ መስኮች የተመዘገቡ ዲፕሎማሲያዊ ስኬቶችም ኢትዮጵያ በአፍሪካ ቀንድ እና በምሥራቅ አፍሪካ እየተጠናከረ የመጣ የኃይል ማዕከል መሆኗን አመላክተዋል።
የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ከመጀመሪያው ቀን ጀምሮ ከፍተኛ ዓለም አቀፍ ትኩረት የሳበ ፕሮጀክት ነበር።
በተለይም የዓባይ ውሃ አጠቃቀምን በተመለከተ በታሪክ የተፈጠሩ የፖለቲካ እና የጂኦፖለቲካ አለመግባባቶች ግድቡን ከቀላል የልማት ፕሮጀክት ወደ የዲፕሎማሲ ፈተና ቀይረውት ነበር።
ሆኖም ኢትዮጵያ “ፍትሐዊና ምክንያታዊ የውሃ አጠቃቀም” እንዲሁም “በሌሎች ላይ ጉልህ ጉዳት አለማድረስ” በሚሉ ዓለም አቀፍ መርሆዎች ላይ ተመስርታ የተከተለችው የዲፕሎማሲ መንገድ ትልቅ ውጤቶችን አስመዝግቧል።
ከተመዘገቡት ታላላቅ ድሎች አንዱ የግድቡ ጉዳይ በአፍሪካ ሕብረት ማዕቀፍ እንዲመራ ማድረግ ነው።
ጉዳዩን ወደ ዓለም አቀፍ የፖለቲካ መድረኮች በመውሰድ ጫና ለመፍጠር የተደረጉ ጥረቶች ቢኖሩም፣ ኢትዮጵያ የአፍሪካ ችግሮች በአፍሪካውያን መፍትሔ ሊያገኙ ይገባል የሚለውን መርህ በተግባር አስከብራለች።
ይህ የዲፕሎማሲ ድል ለኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ለመላው አፍሪካ የተቋማዊ ነጻነት እና የአህጉራዊ ትብብር ማሳያ ሆኗል።
ሌላው ታላቅ ስኬት የግድቡ ግንባታ በውጭ ጫናዎች ሳይቆም እስከ መጨረሻው የውሃ ሙሌት መድረሱ ነው።
በሕዝብ ገንዘብና በብሔራዊ አንድነት የተገነባው ግድብ የኢትዮጵያን የራስ አቅም እና የውጭ ጫናን የመቋቋም ችሎታ አሳይቷል።
ዛሬ ግድቡ የኤሌክትሪክ ኃይል በማመንጨት ለአጎራባች አገራት ለሚደረገው የኃይል ሽያጭ መሠረት ሆኗል። ይህም ግድቡ የግጭት ምንጭ ሳይሆን የቀጣናዊ ትስስርና የጋራ ልማት መሣሪያ መሆኑን በተግባር አረጋግጧል።
የህዳሴ ግድብ ኢትዮጵያን ከተራ የኤሌክትሪክ አምራች ወደ የቀጣናው የኢነርጂ ማዕከል እየቀየራት ነው። ለጅቡቲ፣ ለኬንያ፣ ለሱዳን እና ለሌሎች አገራት የኃይል አቅርቦት መስፋፋቱ የኢኮኖሚ ትስስርን ከማጠናከሩም በላይ የፖለቲካ መተማመንን እየፈጠረ ነው።
ኢትዮጵያ ከ120 ሚሊዮን በላይ ሕዝብ ያላትና ፈጣን የኢኮኖሚ እድገት እያሳየች ያለች አገር ብትሆንም፣ የባሕር በር አልባ መሆኗ ለንግድ፣ ለኢኮኖሚ እና ለብሔራዊ ደኅንነት ከፍተኛ ፈተና ሆኖ ቆይቷል።
በቅርብ ዓመታት ግን ኢትዮጵያ የባሕር በር ጥያቄዋን ከታሪካዊ ቅሬታ ወደ ስትራቴጂካዊ ዲፕሎማሲ ቀይራለች።
ከሶማሊላንድ ጋር የተፈረመው የመግባቢያ ሰነድ (MoU) በዚህ ረገድ ታሪካዊ እርምጃ ተብሎ ይታያል። ይህ እርምጃ ኢትዮጵያ የባሕር በር ፍላጎቷን በሰላማዊ እና በዲፕሎማሲያዊ መንገድ ለማሳካት ያላትን ቁርጠኝነት አሳይቷል።
ይህ የዲፕሎማሲ አቅጣጫ ኢትዮጵያ ከአንድ ወደብ ብቻ ጥገኛ የመሆን አደጋን ለመቀነስና የንግድ ወጪዋን ለመቆጣጠር የሚያስችል አዲስ የጂኦኢኮኖሚ አስተሳሰብ እንዳላት አሳይቷል።
ቀይ ባህር ከዓለም አቀፍ የንግድ መስመሮች አንዱ እንደመሆኑ መጠን በዚህ አካባቢ የሚፈጠሩ የደኅንነት ችግሮች በቀጥታ ኢትዮጵያን ይነካሉ።
በመሆኑም ኢትዮጵያ በቀይ ባህር ጉዳይ ተመልካች ሳይሆን ንቁ ባለድርሻ መሆን እንዳለባት በዲፕሎማሲ መድረኮች ላይ በግልጽ ማስቀመጥ ችላለች። ይህም የአገሪቱን የጂኦፖለቲካ ተጽዕኖ እያሳደገ ነው።
የህዳሴ ግድብና የቀይ ባህር ዲፕሎማሲ በተለያዩ ጉዳዮች ዙሪያ ቢመስሉም፣ የጋራ ዓላማ አላቸው። ይህም ኢትዮጵያን በኢኮኖሚ፣ በኢነርጂ እና በጂኦፖለቲካ የቀጣናው የኃይል ማዕከል ማድረግ ነው።
የህዳሴ ግድብ የኢነርጂ ተጽዕኖን ሲፈጥር፣ የቀይ ባህር ዲፕሎማሲ ደግሞ የንግድና የስትራቴጂካዊ ተደራሽነትን ያጠናክራል። ሁለቱም ተደጋጋፊ ሲሆኑ የኢትዮጵያን የወደፊት ኢኮኖሚ እና የፖለቲካ ኃይል ለመገንባት ወሳኝ ሚና አላቸው።
በህዳሴ ግድብና በቀይ ባህር ጉዳዮች ዙሪያ የታዩት የዲፕሎማሲ ስኬቶች ኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅሞቿን በውይይት፣ በጽናት እና በስትራቴጂካዊ አመራር ማስከበር እንደምትችል አረጋግጠዋል።
ይሁን እንጂ እነዚህ ድሎች ዘላቂ ውጤት እንዲያመጡ የውስጥ አንድነትን ማጠናከር፣ ከጎረቤት አገራት ጋር በጋራ ተጠቃሚነት ላይ የተመሠረተ ግንኙነት መገንባት እና የሰላም ዲፕሎማሲን ማስቀጠል አስፈላጊ ነው።
የህዳሴ ግድብ የኢነርጂ ነፃነትን ሲያመጣ፣ የቀይ ባህር ዲፕሎማሲ ደግሞ የኢትዮጵያን የጂኦፖለቲካ ተደራሽነት ያሰፋል። ሁለቱም ተደምረው ኢትዮጵያን በአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ ተጽዕኖ ፈጣሪ አገር ወደማድረግ እየመሯት ነው።
ውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር
4 days ago
የእንግሊዝ የጉዞ ማሳሰቢያ‼️
ብሪታንያ ወደ ኢትዮጵያ ለሚጓዙ ዜጎቿ የጉዞ ማሳሰቢያ ሰጠች‼️
የብሪታንያ መንግስት ዛሬ ባወጣው የጉዞ ማሳሰቢያ ነገ የሚካሄደውን የኢትዮጵያ ጠቅላላ ምርጫ ተከትሎ ዜጎቿ ወደ ተለያዩ የኢትዮጵያ አካባቢዎች እንዳይጓዙ አስጠንቅቋል።
ማስጠንቀቂያው አብዛኛውን የኢትዮጵያ ክፍል ለጉዞ አደገኛ አድርጎ በመጥቀስ ዜጎቹ ወደ ትግራይ፣ አማራ፣በአፋር እና ጋምቤላ ክልሎች ሙሉ በሙሉ እና ኢትዮጵያ ከጎረቤት ሀገራት በምትዋሰንባቸው የድንበር አካባቢዎች ከአሥር እስከ አንድ መቶ ኪሎ ሜትር ርቀት ውስጥ ማንኛውም ዜጋ እንዳይንቀሳቀስ አሳስቧል።
በኦሮሚያ ክልል ከዋና ዋና መንገዶች እና ከተሞች በስተቀር ከኬንያ ጋር በሚያዋስነው ድንበር በ10 ኪ.ሜ ርቀት ላይ በምዕራብ ሸዋ ፣በሰሜን ሸዋ ዞን ምዕራብ ዋናውን የአዲስ አበባ ወደ ጋምቤላ የሚወስደውን መንገድ ጨምሮ ምዕራብ ወለጋ እና ምስራቅ ወለጋ ዞን፣ ቄለምም ወለጋ እና ሆሮ ጉድሩ ወለጋ እንዳይጓዙ አሳስቧል።
ከአዲስ አበባ እስከ አዳማ ካለው የፍጥነት መንገድ በስተቀር የምስራቅ ሸዋ ዞንም ማስጠንቀቂያ ከወጣባቸው ቦታዎች መካከል አንዱ ነው።
በሶማሌ ክልል ሲቲ ዞን፤ በቤኒሻንጉል-ጉሙዝ ክልል ደግሞ ከሱዳን ጋር ባለው ድንበር በ20 ኪ.ሜ ርቀት ላይ የሜተከል ዞን የማኦኮሞ ልዩ ዞን አስፈላጊ ካልሆነ በስተቀር ሁሉንም ጉዞዎች እንዳይደረግ ይመክራል።
ሰኞ ግንቦት 24 ቀን 2018 በሚካሄደው ምርጫ ምክንያት የህዝብ እንደ ባንኮች ያሉ የአገልግሎት መስጫ ተቋማት ስለሚዘጉ ከወዲሁ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ አሳስቧል።
በምርጫ ጣቢያዎች ዙሪያ ከፍተኛ ጥበቃ ይደረግላቸዋል፣ እንዲሁም የተሽከርካሪና የመታወቂያ ፍተሻዎች ይኖራሉ ብሏል።
አላስፈላጊ ጉዞዎችን ከማድረግ እንዲቆጠቡ ፣ከአካባቢው ባለስልጣናት የተሰጡ መመሪያዎችን እንዲከተሉ እና እና መታወቂያ እንዲይዙ ዜጎቹን አሳስቧል።
Seledadotio
Seledadotio
ብሪታንያ ወደ ኢትዮጵያ ለሚጓዙ ዜጎቿ የጉዞ ማሳሰቢያ ሰጠች‼️
የብሪታንያ መንግስት ዛሬ ባወጣው የጉዞ ማሳሰቢያ ነገ የሚካሄደውን የኢትዮጵያ ጠቅላላ ምርጫ ተከትሎ ዜጎቿ ወደ ተለያዩ የኢትዮጵያ አካባቢዎች እንዳይጓዙ አስጠንቅቋል።
ማስጠንቀቂያው አብዛኛውን የኢትዮጵያ ክፍል ለጉዞ አደገኛ አድርጎ በመጥቀስ ዜጎቹ ወደ ትግራይ፣ አማራ፣በአፋር እና ጋምቤላ ክልሎች ሙሉ በሙሉ እና ኢትዮጵያ ከጎረቤት ሀገራት በምትዋሰንባቸው የድንበር አካባቢዎች ከአሥር እስከ አንድ መቶ ኪሎ ሜትር ርቀት ውስጥ ማንኛውም ዜጋ እንዳይንቀሳቀስ አሳስቧል።
በኦሮሚያ ክልል ከዋና ዋና መንገዶች እና ከተሞች በስተቀር ከኬንያ ጋር በሚያዋስነው ድንበር በ10 ኪ.ሜ ርቀት ላይ በምዕራብ ሸዋ ፣በሰሜን ሸዋ ዞን ምዕራብ ዋናውን የአዲስ አበባ ወደ ጋምቤላ የሚወስደውን መንገድ ጨምሮ ምዕራብ ወለጋ እና ምስራቅ ወለጋ ዞን፣ ቄለምም ወለጋ እና ሆሮ ጉድሩ ወለጋ እንዳይጓዙ አሳስቧል።
ከአዲስ አበባ እስከ አዳማ ካለው የፍጥነት መንገድ በስተቀር የምስራቅ ሸዋ ዞንም ማስጠንቀቂያ ከወጣባቸው ቦታዎች መካከል አንዱ ነው።
በሶማሌ ክልል ሲቲ ዞን፤ በቤኒሻንጉል-ጉሙዝ ክልል ደግሞ ከሱዳን ጋር ባለው ድንበር በ20 ኪ.ሜ ርቀት ላይ የሜተከል ዞን የማኦኮሞ ልዩ ዞን አስፈላጊ ካልሆነ በስተቀር ሁሉንም ጉዞዎች እንዳይደረግ ይመክራል።
ሰኞ ግንቦት 24 ቀን 2018 በሚካሄደው ምርጫ ምክንያት የህዝብ እንደ ባንኮች ያሉ የአገልግሎት መስጫ ተቋማት ስለሚዘጉ ከወዲሁ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ አሳስቧል።
በምርጫ ጣቢያዎች ዙሪያ ከፍተኛ ጥበቃ ይደረግላቸዋል፣ እንዲሁም የተሽከርካሪና የመታወቂያ ፍተሻዎች ይኖራሉ ብሏል።
አላስፈላጊ ጉዞዎችን ከማድረግ እንዲቆጠቡ ፣ከአካባቢው ባለስልጣናት የተሰጡ መመሪያዎችን እንዲከተሉ እና እና መታወቂያ እንዲይዙ ዜጎቹን አሳስቧል።
Seledadotio
Seledadotio
Sponsored by
Surafel
4 days ago
ደቡብ ሱዳን በድንበሯ ላይ የተገነባውን
የግብፅ ጦር ሠፈር እንዲዘጋ አዘዘች
የደቡብ ሱዳን መንግሥት፣ ግብፅ በኢትዮጵያ ድንበር አቅራቢያ በሚገኘው የላይኛው ናይል ግዛት ፓጋክ አካባቢ ያቋቋመችውን ወታደራዊ ጦር ሠፈር በአስቸኳይ እንድትዘጋ ማዘዙን የዓረብኛ የዜና ምንጮች በሰፊው ዘግበዋል።
ይህ በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል አቅራቢያ የተገነባውና ወታደራዊ ሥልጠና የመስጠት እንዲሁም የናይል ወንዝ ፍሰትን የመቆጣጠር ስውር ዓላማ የነበረው ጦር ሠፈር፣ የሥልጠና ባለሙያዎችን ጨምሮ 260 የሚያህል የሰው ኃይል አሰማርቶ የነበረ መሆኑ ታውቋል።
Seledadotio
Seledadotio
የግብፅ ጦር ሠፈር እንዲዘጋ አዘዘች
የደቡብ ሱዳን መንግሥት፣ ግብፅ በኢትዮጵያ ድንበር አቅራቢያ በሚገኘው የላይኛው ናይል ግዛት ፓጋክ አካባቢ ያቋቋመችውን ወታደራዊ ጦር ሠፈር በአስቸኳይ እንድትዘጋ ማዘዙን የዓረብኛ የዜና ምንጮች በሰፊው ዘግበዋል።
ይህ በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል አቅራቢያ የተገነባውና ወታደራዊ ሥልጠና የመስጠት እንዲሁም የናይል ወንዝ ፍሰትን የመቆጣጠር ስውር ዓላማ የነበረው ጦር ሠፈር፣ የሥልጠና ባለሙያዎችን ጨምሮ 260 የሚያህል የሰው ኃይል አሰማርቶ የነበረ መሆኑ ታውቋል።
Seledadotio
Seledadotio
10 days ago
11 days ago
ኢትዮጵያን ጨምሮ አስር አገራት በኢቦላ ቫይረስ የመጠቃት ስጋት አላቸው‼️
የአፍሪካ ህብረት የጤና ኤጀንሲ ኢትዮጵያን ጨምሮ አስር አገራት በኢቦላ ቫይረስ የመጠቃት ስጋት እንዳለባቸዉ አስጠነቀቀ።
ኢትዮጵያን፣ ኬንያን፣ ሩዋንዳንና ደቡብ ሱዳንን ጨምሮ አስር ሀገራት በኢቦላ ቫይረስ የመጠቃት ስጋት እንዳለባቸው ህብረቱ አስጠንቅቋል፡፡
የዓለም ጤና ድርጅት በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ያለውን የኢቦላ ስጋት ወደ ከፍተኛው ደረጃ ከፍ ማድረጉን ተከትሎ፣ የአፍሪካ ህብረት ቫይረሱ 10 አገሮችን ሊያጠቃ እንደሚችል በማስጠንቀቅ ላይ ይገኛል።
ወረርሽኙ ለመጀመሪያ ጊዜ የተገኘው በኢቱሪ ግዛት ሲሆን፤ አካባቢው አስቀድሞም የትጥቅ ግጭቶችና ሰብዓዊ ቀውሶች የሚታዩበት ነው።
በቫይረሱ ከተያዙ ሰዎች ጋር ቀጥተኛ ወይም የቅርብ ንክኪን ማስወገድ የበሽታውን ስርጭት ለመቀነስና ወረርሽኙን ለመቆጣጠር ወሳኝ እርምጃ ነው።
እንደ ዓለም ጤና ድርጅት መረጃ ከሆነ፤ እስካሁን በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ 82 የተረጋገጡ ህመምተኞች እና ሰባት የሞቱ ሰዎች የተመዘገቡ ሲሆን፤ በተጨማሪም ወደ 7መቶ50 የሚጠጉ ኬዞች እና 1መቶ77 በኢቦላ ምክንያት ተከስተዋል ተብለዉ የተጠረጠሩ ሞቶች እንዳሉ ተገልጿል፡፡
በምስራቅ በኩል ከኮንጎ ጋር የምትዋሰነው ኡጋንዳ አምስት የኢቦላ ተጠቂዎችን አረጋግጣለች።
የአፍሪካ ህብረት የጤና ኤጀንሲ ትናንት ባወጣዉ መግለጫ፤ኢትዮጵያን፣ ኬንያን፣ ሩዋንዳንና ደቡብ ሱዳንን ጨምሮ አስር ሀገራት በኢቦላ ቫይረስ የመጠቃት ስጋት እንዳለባቸው አስጠንቅቋል።
Seledadotio
Seledadotio
የአፍሪካ ህብረት የጤና ኤጀንሲ ኢትዮጵያን ጨምሮ አስር አገራት በኢቦላ ቫይረስ የመጠቃት ስጋት እንዳለባቸዉ አስጠነቀቀ።
ኢትዮጵያን፣ ኬንያን፣ ሩዋንዳንና ደቡብ ሱዳንን ጨምሮ አስር ሀገራት በኢቦላ ቫይረስ የመጠቃት ስጋት እንዳለባቸው ህብረቱ አስጠንቅቋል፡፡
የዓለም ጤና ድርጅት በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ያለውን የኢቦላ ስጋት ወደ ከፍተኛው ደረጃ ከፍ ማድረጉን ተከትሎ፣ የአፍሪካ ህብረት ቫይረሱ 10 አገሮችን ሊያጠቃ እንደሚችል በማስጠንቀቅ ላይ ይገኛል።
ወረርሽኙ ለመጀመሪያ ጊዜ የተገኘው በኢቱሪ ግዛት ሲሆን፤ አካባቢው አስቀድሞም የትጥቅ ግጭቶችና ሰብዓዊ ቀውሶች የሚታዩበት ነው።
በቫይረሱ ከተያዙ ሰዎች ጋር ቀጥተኛ ወይም የቅርብ ንክኪን ማስወገድ የበሽታውን ስርጭት ለመቀነስና ወረርሽኙን ለመቆጣጠር ወሳኝ እርምጃ ነው።
እንደ ዓለም ጤና ድርጅት መረጃ ከሆነ፤ እስካሁን በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ 82 የተረጋገጡ ህመምተኞች እና ሰባት የሞቱ ሰዎች የተመዘገቡ ሲሆን፤ በተጨማሪም ወደ 7መቶ50 የሚጠጉ ኬዞች እና 1መቶ77 በኢቦላ ምክንያት ተከስተዋል ተብለዉ የተጠረጠሩ ሞቶች እንዳሉ ተገልጿል፡፡
በምስራቅ በኩል ከኮንጎ ጋር የምትዋሰነው ኡጋንዳ አምስት የኢቦላ ተጠቂዎችን አረጋግጣለች።
የአፍሪካ ህብረት የጤና ኤጀንሲ ትናንት ባወጣዉ መግለጫ፤ኢትዮጵያን፣ ኬንያን፣ ሩዋንዳንና ደቡብ ሱዳንን ጨምሮ አስር ሀገራት በኢቦላ ቫይረስ የመጠቃት ስጋት እንዳለባቸው አስጠንቅቋል።
Seledadotio
Seledadotio
11 days ago
የአፍሪካ ህብረት የጤና ኤጀንሲ ኢትዮጵያን ጨምሮ አስር አገራት በኢቦላ ቫይረስ የመጠቃት ስጋት እንዳለባቸዉ አስጠነቀቀ
ኢትዮጵያን፣ ኬንያን፣ ሩዋንዳንና ደቡብ ሱዳንን ጨምሮ አስር ሀገራት በኢቦላ ቫይረስ የመጠቃት ስጋት እንዳለባቸው ህብረቱ አስጠንቅቋል፡፡
የዓለም ጤና ድርጅት በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ያለውን የኢቦላ ስጋት ወደ ከፍተኛው ደረጃ ከፍ ማድረጉን ተከትሎ፣ የአፍሪካ ህብረት ቫይረሱ 10 አገሮችን ሊያጠቃ እንደሚችል በማስጠንቀቅ ላይ ይገኛል።
ወረርሽኙ ለመጀመሪያ ጊዜ የተገኘው በኢቱሪ ግዛት ሲሆን፤ አካባቢው አስቀድሞም የትጥቅ ግጭቶችና ሰብዓዊ ቀውሶች የሚታዩበት ነው።
በቫይረሱ ከተያዙ ሰዎች ጋር ቀጥተኛ ወይም የቅርብ ንክኪን ማስወገድ የበሽታውን ስርጭት ለመቀነስና ወረርሽኙን ለመቆጣጠር ወሳኝ እርምጃ ነው።
እንደ ዓለም ጤና ድርጅት መረጃ ከሆነ፤ እስካሁን በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ 82 የተረጋገጡ ህመምተኞች እና ሰባት የሞቱ ሰዎች የተመዘገቡ ሲሆን፤ በተጨማሪም ወደ 7መቶ50 የሚጠጉ ኬዞች እና 1መቶ77 በኢቦላ ምክንያት ተከስተዋል ተብለዉ የተጠረጠሩ ሞቶች እንዳሉ ተገልጿል፡፡
በምስራቅ በኩል ከኮንጎ ጋር የምትዋሰነው ኡጋንዳ አምስት የኢቦላ ተጠቂዎችን አረጋግጣለች።
የአፍሪካ ህብረት የጤና ኤጀንሲ ትናንት ባወጣዉ መግለጫ፤ኢትዮጵያን፣ ኬንያን፣ ሩዋንዳንና ደቡብ ሱዳንን ጨምሮ አስር ሀገራት በኢቦላ ቫይረስ የመጠቃት ስጋት እንዳለባቸው አስጠንቅቋል።
እስከዳር ግርማ
ኢትዮጵያን፣ ኬንያን፣ ሩዋንዳንና ደቡብ ሱዳንን ጨምሮ አስር ሀገራት በኢቦላ ቫይረስ የመጠቃት ስጋት እንዳለባቸው ህብረቱ አስጠንቅቋል፡፡
የዓለም ጤና ድርጅት በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ያለውን የኢቦላ ስጋት ወደ ከፍተኛው ደረጃ ከፍ ማድረጉን ተከትሎ፣ የአፍሪካ ህብረት ቫይረሱ 10 አገሮችን ሊያጠቃ እንደሚችል በማስጠንቀቅ ላይ ይገኛል።
ወረርሽኙ ለመጀመሪያ ጊዜ የተገኘው በኢቱሪ ግዛት ሲሆን፤ አካባቢው አስቀድሞም የትጥቅ ግጭቶችና ሰብዓዊ ቀውሶች የሚታዩበት ነው።
በቫይረሱ ከተያዙ ሰዎች ጋር ቀጥተኛ ወይም የቅርብ ንክኪን ማስወገድ የበሽታውን ስርጭት ለመቀነስና ወረርሽኙን ለመቆጣጠር ወሳኝ እርምጃ ነው።
እንደ ዓለም ጤና ድርጅት መረጃ ከሆነ፤ እስካሁን በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ 82 የተረጋገጡ ህመምተኞች እና ሰባት የሞቱ ሰዎች የተመዘገቡ ሲሆን፤ በተጨማሪም ወደ 7መቶ50 የሚጠጉ ኬዞች እና 1መቶ77 በኢቦላ ምክንያት ተከስተዋል ተብለዉ የተጠረጠሩ ሞቶች እንዳሉ ተገልጿል፡፡
በምስራቅ በኩል ከኮንጎ ጋር የምትዋሰነው ኡጋንዳ አምስት የኢቦላ ተጠቂዎችን አረጋግጣለች።
የአፍሪካ ህብረት የጤና ኤጀንሲ ትናንት ባወጣዉ መግለጫ፤ኢትዮጵያን፣ ኬንያን፣ ሩዋንዳንና ደቡብ ሱዳንን ጨምሮ አስር ሀገራት በኢቦላ ቫይረስ የመጠቃት ስጋት እንዳለባቸው አስጠንቅቋል።
እስከዳር ግርማ
13 days ago
ሌተና ጄኔራል አልብሩሀን ከዩናይትድ አረብ ኤመሬትስ ጋር ለመነጋገር ፈቃደኛ መሆናቸውን አስታወቁ፡፡
የሱዳን ወታደራዊ መንግስት መሪ የሆኑት ሌተና ጄኔራል አብዱል ፈታህ አልብሩሀን ከዩናይትድ አረብ ኤመሬትስ ጋር ለመነጋገር ፈቃደኝነታቸውን ገልፀው ቅድመ ሁኔታዎችን ግን አስቀምጠዋል፡፡
ጄኔራሉ ከሚድል ኢስት አይ ጋር ባደረጉት ቃለምልልስ ሲናገሩ ‹‹እኛ ከዩናይትድ አረብ ኤመሬትስ ጋር የሰላም ንግግር ለመጀመር ፈቃደኛ ነን፡፡
ይሁንና ይህንን ንግግር ለመጀመር ሱዳን የሱዳን ፍላጎቶች መሟላት ይኖርባቸዋል፡፡
ዩናይትድ አረብ ኤመሬትስ የሱዳንን አንድነት ማክበር ይጠበቅባታል፣ለሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ጦር የምታደርገውን ወታደራዊ ድጋፍ ታቁም ብለዋል፡፡
የጋዜጣው ምንጮች እንደገለፁት ባለፈው ሳምንት አልብሩሀን ወደባህሬን የተጓዙት ባህሬን በሱዳንና በኤመሬትስ መካከል ንግግር እንዲጀመር እያደረገችው ያለው ጥረት አካል ነበር፡፡
በኤመሬትስና በሱዳን መካከል ቀጥተኛ ዲፕሎማሲያዊ መስመር እንዲከፈት የተደረገው ሙከራ እስካሁን ሊሳካ አለመቻሉንም አስታውቋል፡፡
የሱዳን መንግስት ኤመሬትስ ለፈጥኖ ደራሽ ሀይሉ የምትሰጠውን ጦር መሳሪያ ድጋፍ እንድታቋርጥ አቋም መያዙን የገለፀው ዘገባው ቀጥተኛ ንግግር ለማድረግ ይህንን እንደ ቅድመ ሁኔታ ማስቀመጡንም አስረድቷል፡፡
seledadotio
seledadotio
የሱዳን ወታደራዊ መንግስት መሪ የሆኑት ሌተና ጄኔራል አብዱል ፈታህ አልብሩሀን ከዩናይትድ አረብ ኤመሬትስ ጋር ለመነጋገር ፈቃደኝነታቸውን ገልፀው ቅድመ ሁኔታዎችን ግን አስቀምጠዋል፡፡
ጄኔራሉ ከሚድል ኢስት አይ ጋር ባደረጉት ቃለምልልስ ሲናገሩ ‹‹እኛ ከዩናይትድ አረብ ኤመሬትስ ጋር የሰላም ንግግር ለመጀመር ፈቃደኛ ነን፡፡
ይሁንና ይህንን ንግግር ለመጀመር ሱዳን የሱዳን ፍላጎቶች መሟላት ይኖርባቸዋል፡፡
ዩናይትድ አረብ ኤመሬትስ የሱዳንን አንድነት ማክበር ይጠበቅባታል፣ለሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ጦር የምታደርገውን ወታደራዊ ድጋፍ ታቁም ብለዋል፡፡
የጋዜጣው ምንጮች እንደገለፁት ባለፈው ሳምንት አልብሩሀን ወደባህሬን የተጓዙት ባህሬን በሱዳንና በኤመሬትስ መካከል ንግግር እንዲጀመር እያደረገችው ያለው ጥረት አካል ነበር፡፡
በኤመሬትስና በሱዳን መካከል ቀጥተኛ ዲፕሎማሲያዊ መስመር እንዲከፈት የተደረገው ሙከራ እስካሁን ሊሳካ አለመቻሉንም አስታውቋል፡፡
የሱዳን መንግስት ኤመሬትስ ለፈጥኖ ደራሽ ሀይሉ የምትሰጠውን ጦር መሳሪያ ድጋፍ እንድታቋርጥ አቋም መያዙን የገለፀው ዘገባው ቀጥተኛ ንግግር ለማድረግ ይህንን እንደ ቅድመ ሁኔታ ማስቀመጡንም አስረድቷል፡፡
seledadotio
seledadotio
Sponsored by
Surafel
14 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) ሌተና ጄኔራል አልብሩሀን ከዩናይትድ አረብ ኤመሬትስ ጋር ለመነጋገር ፈቃደኛ መሆናቸውን አስታወቁ፡፡ የሱዳን ወታደራዊ መንግስት መሪ የሆኑት ሌተና ጄኔራል አብዱል ፈታህ አልብሩሀን ከዩናይትድ አረብ ኤመሬትስ ጋር ለመነጋገር ፈቃደኝነታቸውን ገልፀው ቅድመ ሁኔታዎችን ግን አስቀምጠዋል፡፡
ጄኔራሉ ከሚድል ኢስት አይ ጋር ባደረጉት ቃለምልልስ ሲናገሩ ‹‹እኛ ከዩናይትድ አረብ ኤመሬትስ ጋር የሰላም ንግግር ለመጀመር ፈቃደኛ ነን፡፡ ይሁንና ይህንን ንግግር ለመጀመር ሱዳን የሱዳን ፍላጎቶች መሟላት ይኖርባቸዋል፡፡ ዩናይትድ አረብ ኤመሬትስ የሱዳንን አንድነት ማክበር ይጠበቅባታል›› ብለዋል፡፡ የጋዜጣው ምንጮች እንደገለፁት ባለፈው ሳምንት አልብሩሀን ወደባህሬን የተጓዙት ባህሬን በሱዳንና በኤመሬትስ መካከል ንግግር እንዲጀመር እያደረገችው ያለው ጥረት አካል ነበር፡፡ በኤመሬትስና በሱዳን መካከል ቀጥተኛ ዲፕሎማሲያዊ መስመር እንዲከፈት የተደረገው ሙከራ እስካሁን ሊሳካ አለመቻሉንም አስታውቋል፡፡ የሱዳን መንግስት ኤመሬትስ ለፈጥኖ ደራሽ ሀይሉ የምትሰጠውን ጦር መሳሪያ ድጋፍ እንድታቋርጥ አቋም መያዙን የገለፀው ዘገባው ቀጥተኛ ንግግር ለማድረግ ይህንን እንደ ቅድመ ሁኔታ ማስቀመጡንም አስረድቷል፡፡
ጄኔራሉ ከሚድል ኢስት አይ ጋር ባደረጉት ቃለምልልስ ሲናገሩ ‹‹እኛ ከዩናይትድ አረብ ኤመሬትስ ጋር የሰላም ንግግር ለመጀመር ፈቃደኛ ነን፡፡ ይሁንና ይህንን ንግግር ለመጀመር ሱዳን የሱዳን ፍላጎቶች መሟላት ይኖርባቸዋል፡፡ ዩናይትድ አረብ ኤመሬትስ የሱዳንን አንድነት ማክበር ይጠበቅባታል›› ብለዋል፡፡ የጋዜጣው ምንጮች እንደገለፁት ባለፈው ሳምንት አልብሩሀን ወደባህሬን የተጓዙት ባህሬን በሱዳንና በኤመሬትስ መካከል ንግግር እንዲጀመር እያደረገችው ያለው ጥረት አካል ነበር፡፡ በኤመሬትስና በሱዳን መካከል ቀጥተኛ ዲፕሎማሲያዊ መስመር እንዲከፈት የተደረገው ሙከራ እስካሁን ሊሳካ አለመቻሉንም አስታውቋል፡፡ የሱዳን መንግስት ኤመሬትስ ለፈጥኖ ደራሽ ሀይሉ የምትሰጠውን ጦር መሳሪያ ድጋፍ እንድታቋርጥ አቋም መያዙን የገለፀው ዘገባው ቀጥተኛ ንግግር ለማድረግ ይህንን እንደ ቅድመ ሁኔታ ማስቀመጡንም አስረድቷል፡፡
14 days ago
የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን የኢትዮጵያውያን ስደተኞችን ሰብዓዊ ክብር እና ሕይወት በተመለከተ የተላለፈ ሐዋርያዊ ጥሪ
“ምሕረት የሚያደርጉ ብፁዓን ናቸው፤ ምሕረትን ያገኛሉና”. (ማቴ 5:7)
ለፖለቲካ መሪዎች፣ የሃይማኖት መሪዎች፣ የሰብአዊ መብት ድርጅቶች፣ የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች፣ ሚዲያዎች እና በጎ ፈቃድ ላላቸው ሰዎች ሁሉ
የተከበራችሁ ወንድሞች እና እህቶች
እኛ የኢትዮጵያ ካቶሊክ ጳጳሳት በመላው አለም ስለሚገኙ ኢትዮጵያውያን ስደተኞች ወቅታዊ ሁኔታች እንዳሳሰበን ለመግለጽ እንፈልጋለን። በአገራችን በሚሊዮን የሚቆጠሩ ወጣት ወንዶችና ሴቶች አገራቸውን ለቀው የሚወጡት ለአገራቸው ፍቅር በማጣት ሳይሆን፣ የተሻለ የሥራ ዕድል እና የኑሮ ሁኔታ በመፈለግ ነው። ተነሳሽነታቸው እጅግ ሊከበር የሚገባው እና መስዋዕትነት የሚጠይቅ ነው፤ ይህም ህይወታቸውን ለማሻሻል፣ ቤተሰቦቻቸውን ለመደገፍ እና በመጨረሻም ለአገራቸው እድገት አስተዋጽኦ ለማድረግ ነው። ነገር ግን እጅግ በሚያሳዝን ሁኔታ፣ ስደተኞቻችን የሚያስፈልጋቸውን ሰብዓዊ ክብር ከማግኘት ይልቅ በመዋቅራዊ ብዝበዛ፣ በፍርሃት፣ በገለልተኝነት እና በከባድ ተጋላጭነት ወጥመድ ውስጥ ይገባሉ። ሁኔታቸው ምንም ያህል ተስፋ አስቆራጭ ቢሆንም፣ ቅዱስ የሆነው ሰብአዊ ክብራቸው ግን በድንበር፣ በሕጋዊ ሁኔታ ወይም በኢኮኖሚ ስርዓት ችላ ሊባል ወይም ሊጠፋ አይችልም።
የካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ትምህርተ ክርስቶስ እንዲህ ይላል፤ “በኢኮኖሚ የበለጸጉ መንግስታት፣ ሰዎች በትውልድ አገራቸው ጸጥታንና ለመተዳድሪያ የሚሆን ገቢ በማጣታቸው ወደ አገራቸው ሲገቡ ተቀብለው የተቻላቸውን እርዳታ መስጠት አለባቸው” (CCC 2241)። ይህ ትምህርት ስደተኞች እንደ ውጭ ወይም እንደሸክም መታየት እንደሌለባቸው ይልቁንም እንደ ወንድምና እህት ሰብዓዊ ክብራቸው ሊከበርና ሊጠበቅ እንደሚገባ ያስተምረናል።
ይሁን እንጂ፣ ብዙ ስደተኞች በስደት ጉዟቸው ወቅት ከባድ ፈተናዎች ያጋጥሟቸዋል፤ በእጅጉም ይሰቃያሉ። እኛም ከዚህ በታች የተገለጹትን ቁልፍ የስደት መዳረሻዎች እና ወንድሞቻችን እና እህቶቻችን የሚያጋጥሟቸውን ተያያዥ ችግሮች ተመልክተናል።
1) አንዳንድ የመካከለኛው ምስራቅ አገሮች፡-
• ሳውዲ አረቢያ፡- በሳውዲ አረቢያ መንግሥት የሚኖሩ ብዙ ኢትዮጵያዊያን ስደተኞች አሉ። የኢትዮጵያ የካቶሊክ ጳጳሳት ጉባኤ በተለያዩ የሚዲያ ዘገባዎች በሰማነው መሰረት በመቶዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያዊያን ዜጎች ላይ በተፈረደው የሞት ፍርድ ያለንን ስጋት፣ የተሰማንን ጥልቅ ሀዘን እንገልጻለን። የሳውዲ አረቢያ ባለስልጣናት ለዜጎቻችን ሁሉ ርህራሄ እና ምሕረት እንዲያደርጉ ክቡር የሆነውን የሰው ሕይወት እንዲጠብቁ እንጠይቃለን።
• የመን፡- በርካታ ኢትዮጵያዊያን ስደተኞች ወደ የመን ለመግባት ወይም ወደ ሳውዲ አረቢያ ለመጓዝ በቀይ ባህር፣ በጅቡቲ ወይም በኤደን ባሕረ ሰላጤ በኩል ያልፋሉ። የመን ብዙውን ጊዜ ወደ ሌሎች የባህረ ሰላጤ አገሮች እንደ መጓጓዣ መንገድ ትጠቀማለች፤ ሆኖም ግን፣ ብዙ ስደተኞች በመንገድ ላይ ከፍተኛ ሥቃይ ይደርስባቸዋል፣ ዓመፅ፣ በደል እና ኢ-ሰብአዊ ተግባራት ይደርስባቸዋል። በሚያሳዝን ሁኔታ፣ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ስደተኞች በጉዞው አደገኛ ባህሪ እና በሚገጥሟቸው አስቸጋሪ ሁኔታዎች ምክንያት ሕይወታቸውን ያጣሉ።
• ሊባኖስ፡- በሊባኖስ የሚገኙ ብዙ ኢትዮጵያዊያን ስደተኞች በአገሪቱ ውስጥ ባለው ግጭትና አለመረጋጋት ምክንያት ለአደጋ የተጋለጡ ናቸው። በዚህም ምክንያት በርካታ ቁጥር ያላቸው ሰዎች ወደ ትውልድ አገራቸው በሰላም ለመመለስና ከቤተሰቦቻቸው ጋር ለመገናኘት ይፈልጋሉ።
• የባህረ ሰላጤ አገሮች፡- በእነዚህ አገሮች ውስጥ የሚገኙ ብዙ ኢትዮጵያዊያን ስደተኞች በአሌሪካ በእስራኤል እና በኢራን መሃከል በተፈጠረው ጦርነት እና ግጭት ምክንያት በጭንቅ ውስጥ ይገኛሉ።
2) የደቡብ አፍሪካ ሪፐብሊክ ለብዙ ኢትዮጵያዊያን ስደተኞች ሌላ መዳረሻ ናት። ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ኢትዮጵያዊያን ለሕይወታቸውና ለንብረታቸው ከፍተኛ ስጋት ውስጥ ይገኛሉ። አንዳንዶቹ ወደአስቡበት ሳይደርሱ በጉዞ ላይ እያሉ እስራት ይገጥማቸዋል፣ ሌሎቹ ደግሞ ወደ መድረሻቸው የሚደርሱ ሰዎች በፍርሃትና ውስጥ በምኖር ላይ ናቸው። በሚደርሱን ዘገባዎች መሰረት በደቡብ አፍሪካውያን የውጭ ዜጎች ጥላቻ የተነሳ በዓመፅ፣ እና በግድያ በርካታ ኢትዮጵያውያን ስደተኞች ክቡር ሕይወታቸው እየጠፋ ነው።
3) የሱዳን - ሊቢያ - የአውሮፓ መንገድ፡ ይህ መንገድ ለረጅም ጊዜ በሕገወጥ አዘዋዋሪዎች በብዛት ከሚጠቀሙባቸው መንገዶች አንዱ ሲሆን፣ ስፍር ቁጥር ለሌላቸው ስደተኞች ከፍተኛ ስቃይ እና ህልፈተ ህይወት አስከትሏል። ብዙዎች አስቸጋሪ እና አደገኛ የሆነውን የበረሃ መንገድ በኢሰብአዊ ሁኔታዎች ሲያቋርጡ ሕይወታቸውን አጥተዋል። በአሁኑ ጊዜ በሱዳን እየተካሄደ ያለው ግጭት ይህንን ጉዞ የበለጠ አደገኛ አድርጎታል። ሊቢያ የሚደርሱ ሰዎች ብዙውን ጊዜ እስር፣ ዝርፊያ፣ የጉልበት ብዝበዛ እና ከባድ በደል ይደርስባቸዋል። አንዳንዶቹ በክርስትና እምነታቸው ምክንያት ስደት ደርሶባቸዋል እና ህይወታቸውን አጥተዋል። በአደገኛ ጀልባዎች የሜዲትራኒያንን ባህር ለመሻገር የሚሞክሩ ስደተኞች ሲሰምጡ፤ ብዙዎቹ በሚያሳዝን ሁኔታ ህይወታቸውን ያጣሉ፣ ጥቂቶች ብቻ ወደ ላምፔዱዛ ዳርቻ መድረስ ችለዋል። ላምፔዱዛ የቀድሞ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንቼስኮስ በአንድ ወቅት በባህር ላይ ለሞቱት ሰዎች መታሰቢያ የአበባ ጉንጉን አስቀምጠዋል፤ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሌዎ 14ኛም የካቶሊክ ቤተክርስቲያን ለስደተኞች ያላትን አንድነት፣ ርህራሄ እና ለስደተኞች ድምጽ የመሆን ተልዕኮ ለማስቀጠል ደሴቲቱን በቅርቡ እንደሚጎበኙም ይጠበቃል።
ይህ የኢትዮጵያውያን ስደተኞች ስቃይ ከቁጥርም በላይ ውድ እና የተከበረ ህይወት ያላቸው እንዲሁም ቤተሰቦቻቸው በእንባ፣ በመስዋዕትነት እና በተስፋ የሸኟቸው ልጆች ናቸው። ብዙ ጊዜ ግን እነዚህ ስደተኞች በብዝበዛ፣ በፍርሃት፣ በደል፣ በመገለል እና ለጥቃት በመጋለጥ አላስፈላጊ ስርዓቶች ውስጥ ይወድቃሉ። ብዙዎች ለማሰብ አዳጋች በሆኑ ሁኔታዎችን ውስጥ በህይወት ለመቆየት ይታገላሉ።
በክርስቲያያዊ የበጎ አድራጎት እና በዓለም አቀፍ የወንድማማችነት መንፈስ፣ ለሳውዲ አረቢያ መንግሥት ባለሥልጣናት፣ ከኢትዮጵያውያን ጋር በተያያዘ የሚፈጸሙ ማናቸውም የታቀዱ ግድያዎች እንዲቆሙ እና በእነዚህ ጉዳዮች ላይ ምሕረትን እንዲያደርጉ ልመና እናቀርባለን። ምህረት ፍትህን አያዳክምም። ምህረት ፍትህን ከፍ በማድረግ ተስፋ ለቆረጡ ተስፋን ይሰጣል።
ይህ አሳዛኝ ሁኔታ ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ መደበኛ ያልሆነ ፍልሰትን የሚያባብሱትን ጥልቅ ምክንያቶች ከመሰረቱ ለማስወገድ ይተባበር ዘንድ ዕድል የሚሰጥ ሊሆን ይገባል። ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮች፣ የከባቢ አየር ሁኔታ መቃወስ እና ሌሎች ዘርፈ ብዙ ምክንያቶች በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎችን በዓለም ዙሪያ አደገኛ የፍልሰት መንገዶችን እንዲከተሉ እንደሚያስገድዳቸው አስተውለናል። እነዚህን ዋና ዋና ምክንያቶች ችላ የሚል ዓለም የፍልሰት ቀውስን መፍታት አይችልም። በእርግጥም፣ የሰብዓዊነታችን እና የሥልጣኔ መለኪያ በዙሪያችን ያሉ ተጋላጭ ለሆኑ ሰዎች በምናሳሳየው እንክብካቤ ላይ የተመሠረተ ነው።
እንደ ኢትዮጵያ ካቶሊክ ጳጳሳት፣ ውይይት፣ ምሕረትና ጥበብ ተስፋ መቁረጥንና ሞትን እንዲያሸንፉ አጥብቀን መጸለያችንን እንቀጥላለን። እነዚህን ተጋላጭ የሆኑ ኢትዮጵያዊ ስደተኞች፣ ቤተሰቦቻቸውን እና ሁሉንም ውሳኔ ሰጪዎች ለሁሉ ቻይ በሆነው የእግዚአብሔርን አምላክ ምህረት እና እገዛ ያገኙ ዘንድ እንጸልያለን።
የኢትዮጵያ የካቶሊክ ጳጳሳት ጉባኤ
አዲስ አበባ
10/09/2018
“ምሕረት የሚያደርጉ ብፁዓን ናቸው፤ ምሕረትን ያገኛሉና”. (ማቴ 5:7)
ለፖለቲካ መሪዎች፣ የሃይማኖት መሪዎች፣ የሰብአዊ መብት ድርጅቶች፣ የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች፣ ሚዲያዎች እና በጎ ፈቃድ ላላቸው ሰዎች ሁሉ
የተከበራችሁ ወንድሞች እና እህቶች
እኛ የኢትዮጵያ ካቶሊክ ጳጳሳት በመላው አለም ስለሚገኙ ኢትዮጵያውያን ስደተኞች ወቅታዊ ሁኔታች እንዳሳሰበን ለመግለጽ እንፈልጋለን። በአገራችን በሚሊዮን የሚቆጠሩ ወጣት ወንዶችና ሴቶች አገራቸውን ለቀው የሚወጡት ለአገራቸው ፍቅር በማጣት ሳይሆን፣ የተሻለ የሥራ ዕድል እና የኑሮ ሁኔታ በመፈለግ ነው። ተነሳሽነታቸው እጅግ ሊከበር የሚገባው እና መስዋዕትነት የሚጠይቅ ነው፤ ይህም ህይወታቸውን ለማሻሻል፣ ቤተሰቦቻቸውን ለመደገፍ እና በመጨረሻም ለአገራቸው እድገት አስተዋጽኦ ለማድረግ ነው። ነገር ግን እጅግ በሚያሳዝን ሁኔታ፣ ስደተኞቻችን የሚያስፈልጋቸውን ሰብዓዊ ክብር ከማግኘት ይልቅ በመዋቅራዊ ብዝበዛ፣ በፍርሃት፣ በገለልተኝነት እና በከባድ ተጋላጭነት ወጥመድ ውስጥ ይገባሉ። ሁኔታቸው ምንም ያህል ተስፋ አስቆራጭ ቢሆንም፣ ቅዱስ የሆነው ሰብአዊ ክብራቸው ግን በድንበር፣ በሕጋዊ ሁኔታ ወይም በኢኮኖሚ ስርዓት ችላ ሊባል ወይም ሊጠፋ አይችልም።
የካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ትምህርተ ክርስቶስ እንዲህ ይላል፤ “በኢኮኖሚ የበለጸጉ መንግስታት፣ ሰዎች በትውልድ አገራቸው ጸጥታንና ለመተዳድሪያ የሚሆን ገቢ በማጣታቸው ወደ አገራቸው ሲገቡ ተቀብለው የተቻላቸውን እርዳታ መስጠት አለባቸው” (CCC 2241)። ይህ ትምህርት ስደተኞች እንደ ውጭ ወይም እንደሸክም መታየት እንደሌለባቸው ይልቁንም እንደ ወንድምና እህት ሰብዓዊ ክብራቸው ሊከበርና ሊጠበቅ እንደሚገባ ያስተምረናል።
ይሁን እንጂ፣ ብዙ ስደተኞች በስደት ጉዟቸው ወቅት ከባድ ፈተናዎች ያጋጥሟቸዋል፤ በእጅጉም ይሰቃያሉ። እኛም ከዚህ በታች የተገለጹትን ቁልፍ የስደት መዳረሻዎች እና ወንድሞቻችን እና እህቶቻችን የሚያጋጥሟቸውን ተያያዥ ችግሮች ተመልክተናል።
1) አንዳንድ የመካከለኛው ምስራቅ አገሮች፡-
• ሳውዲ አረቢያ፡- በሳውዲ አረቢያ መንግሥት የሚኖሩ ብዙ ኢትዮጵያዊያን ስደተኞች አሉ። የኢትዮጵያ የካቶሊክ ጳጳሳት ጉባኤ በተለያዩ የሚዲያ ዘገባዎች በሰማነው መሰረት በመቶዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያዊያን ዜጎች ላይ በተፈረደው የሞት ፍርድ ያለንን ስጋት፣ የተሰማንን ጥልቅ ሀዘን እንገልጻለን። የሳውዲ አረቢያ ባለስልጣናት ለዜጎቻችን ሁሉ ርህራሄ እና ምሕረት እንዲያደርጉ ክቡር የሆነውን የሰው ሕይወት እንዲጠብቁ እንጠይቃለን።
• የመን፡- በርካታ ኢትዮጵያዊያን ስደተኞች ወደ የመን ለመግባት ወይም ወደ ሳውዲ አረቢያ ለመጓዝ በቀይ ባህር፣ በጅቡቲ ወይም በኤደን ባሕረ ሰላጤ በኩል ያልፋሉ። የመን ብዙውን ጊዜ ወደ ሌሎች የባህረ ሰላጤ አገሮች እንደ መጓጓዣ መንገድ ትጠቀማለች፤ ሆኖም ግን፣ ብዙ ስደተኞች በመንገድ ላይ ከፍተኛ ሥቃይ ይደርስባቸዋል፣ ዓመፅ፣ በደል እና ኢ-ሰብአዊ ተግባራት ይደርስባቸዋል። በሚያሳዝን ሁኔታ፣ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ስደተኞች በጉዞው አደገኛ ባህሪ እና በሚገጥሟቸው አስቸጋሪ ሁኔታዎች ምክንያት ሕይወታቸውን ያጣሉ።
• ሊባኖስ፡- በሊባኖስ የሚገኙ ብዙ ኢትዮጵያዊያን ስደተኞች በአገሪቱ ውስጥ ባለው ግጭትና አለመረጋጋት ምክንያት ለአደጋ የተጋለጡ ናቸው። በዚህም ምክንያት በርካታ ቁጥር ያላቸው ሰዎች ወደ ትውልድ አገራቸው በሰላም ለመመለስና ከቤተሰቦቻቸው ጋር ለመገናኘት ይፈልጋሉ።
• የባህረ ሰላጤ አገሮች፡- በእነዚህ አገሮች ውስጥ የሚገኙ ብዙ ኢትዮጵያዊያን ስደተኞች በአሌሪካ በእስራኤል እና በኢራን መሃከል በተፈጠረው ጦርነት እና ግጭት ምክንያት በጭንቅ ውስጥ ይገኛሉ።
2) የደቡብ አፍሪካ ሪፐብሊክ ለብዙ ኢትዮጵያዊያን ስደተኞች ሌላ መዳረሻ ናት። ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ኢትዮጵያዊያን ለሕይወታቸውና ለንብረታቸው ከፍተኛ ስጋት ውስጥ ይገኛሉ። አንዳንዶቹ ወደአስቡበት ሳይደርሱ በጉዞ ላይ እያሉ እስራት ይገጥማቸዋል፣ ሌሎቹ ደግሞ ወደ መድረሻቸው የሚደርሱ ሰዎች በፍርሃትና ውስጥ በምኖር ላይ ናቸው። በሚደርሱን ዘገባዎች መሰረት በደቡብ አፍሪካውያን የውጭ ዜጎች ጥላቻ የተነሳ በዓመፅ፣ እና በግድያ በርካታ ኢትዮጵያውያን ስደተኞች ክቡር ሕይወታቸው እየጠፋ ነው።
3) የሱዳን - ሊቢያ - የአውሮፓ መንገድ፡ ይህ መንገድ ለረጅም ጊዜ በሕገወጥ አዘዋዋሪዎች በብዛት ከሚጠቀሙባቸው መንገዶች አንዱ ሲሆን፣ ስፍር ቁጥር ለሌላቸው ስደተኞች ከፍተኛ ስቃይ እና ህልፈተ ህይወት አስከትሏል። ብዙዎች አስቸጋሪ እና አደገኛ የሆነውን የበረሃ መንገድ በኢሰብአዊ ሁኔታዎች ሲያቋርጡ ሕይወታቸውን አጥተዋል። በአሁኑ ጊዜ በሱዳን እየተካሄደ ያለው ግጭት ይህንን ጉዞ የበለጠ አደገኛ አድርጎታል። ሊቢያ የሚደርሱ ሰዎች ብዙውን ጊዜ እስር፣ ዝርፊያ፣ የጉልበት ብዝበዛ እና ከባድ በደል ይደርስባቸዋል። አንዳንዶቹ በክርስትና እምነታቸው ምክንያት ስደት ደርሶባቸዋል እና ህይወታቸውን አጥተዋል። በአደገኛ ጀልባዎች የሜዲትራኒያንን ባህር ለመሻገር የሚሞክሩ ስደተኞች ሲሰምጡ፤ ብዙዎቹ በሚያሳዝን ሁኔታ ህይወታቸውን ያጣሉ፣ ጥቂቶች ብቻ ወደ ላምፔዱዛ ዳርቻ መድረስ ችለዋል። ላምፔዱዛ የቀድሞ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንቼስኮስ በአንድ ወቅት በባህር ላይ ለሞቱት ሰዎች መታሰቢያ የአበባ ጉንጉን አስቀምጠዋል፤ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሌዎ 14ኛም የካቶሊክ ቤተክርስቲያን ለስደተኞች ያላትን አንድነት፣ ርህራሄ እና ለስደተኞች ድምጽ የመሆን ተልዕኮ ለማስቀጠል ደሴቲቱን በቅርቡ እንደሚጎበኙም ይጠበቃል።
ይህ የኢትዮጵያውያን ስደተኞች ስቃይ ከቁጥርም በላይ ውድ እና የተከበረ ህይወት ያላቸው እንዲሁም ቤተሰቦቻቸው በእንባ፣ በመስዋዕትነት እና በተስፋ የሸኟቸው ልጆች ናቸው። ብዙ ጊዜ ግን እነዚህ ስደተኞች በብዝበዛ፣ በፍርሃት፣ በደል፣ በመገለል እና ለጥቃት በመጋለጥ አላስፈላጊ ስርዓቶች ውስጥ ይወድቃሉ። ብዙዎች ለማሰብ አዳጋች በሆኑ ሁኔታዎችን ውስጥ በህይወት ለመቆየት ይታገላሉ።
በክርስቲያያዊ የበጎ አድራጎት እና በዓለም አቀፍ የወንድማማችነት መንፈስ፣ ለሳውዲ አረቢያ መንግሥት ባለሥልጣናት፣ ከኢትዮጵያውያን ጋር በተያያዘ የሚፈጸሙ ማናቸውም የታቀዱ ግድያዎች እንዲቆሙ እና በእነዚህ ጉዳዮች ላይ ምሕረትን እንዲያደርጉ ልመና እናቀርባለን። ምህረት ፍትህን አያዳክምም። ምህረት ፍትህን ከፍ በማድረግ ተስፋ ለቆረጡ ተስፋን ይሰጣል።
ይህ አሳዛኝ ሁኔታ ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ መደበኛ ያልሆነ ፍልሰትን የሚያባብሱትን ጥልቅ ምክንያቶች ከመሰረቱ ለማስወገድ ይተባበር ዘንድ ዕድል የሚሰጥ ሊሆን ይገባል። ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮች፣ የከባቢ አየር ሁኔታ መቃወስ እና ሌሎች ዘርፈ ብዙ ምክንያቶች በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎችን በዓለም ዙሪያ አደገኛ የፍልሰት መንገዶችን እንዲከተሉ እንደሚያስገድዳቸው አስተውለናል። እነዚህን ዋና ዋና ምክንያቶች ችላ የሚል ዓለም የፍልሰት ቀውስን መፍታት አይችልም። በእርግጥም፣ የሰብዓዊነታችን እና የሥልጣኔ መለኪያ በዙሪያችን ያሉ ተጋላጭ ለሆኑ ሰዎች በምናሳሳየው እንክብካቤ ላይ የተመሠረተ ነው።
እንደ ኢትዮጵያ ካቶሊክ ጳጳሳት፣ ውይይት፣ ምሕረትና ጥበብ ተስፋ መቁረጥንና ሞትን እንዲያሸንፉ አጥብቀን መጸለያችንን እንቀጥላለን። እነዚህን ተጋላጭ የሆኑ ኢትዮጵያዊ ስደተኞች፣ ቤተሰቦቻቸውን እና ሁሉንም ውሳኔ ሰጪዎች ለሁሉ ቻይ በሆነው የእግዚአብሔርን አምላክ ምህረት እና እገዛ ያገኙ ዘንድ እንጸልያለን።
የኢትዮጵያ የካቶሊክ ጳጳሳት ጉባኤ
አዲስ አበባ
10/09/2018
15 days ago
በምስራቅ አፍሪካ ከፍተኛ የዝናብ እጥረት ሊከሰት እንደሚችል ተገለፀ
ከመጪው ሐምሌ እስከ መስከረም ዓ.ም ባሉት የክረምት ወራት በኢትዮጵያ (በተለይም በመካከለኛው፣ ሰሜንና ምስራቅ አካባቢዎች) እንዲሁም በሱዳን፣ ደቡብ ሱዳን፣ በከፊል ኬንያና ኡጋንዳ ከተለመደው በታች የዝናብ እጥረት ሊከሰት እንደሚችል የኢጋድ አደጋ መከላከል ኃላፊ ዶክተር አሕመድ አምዲሆን አስጠነቀቁ።
በኢትዮጵያ ሜቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት እና በኢጋድ የአየር ጠባይ ትንበያ ማዕከል ትብብር በተዘጋጀው 73ኛው የምስራቅ አፍሪካ የአየር ጠባይ ትንተና እና ትንበያ ጉባኤ ላይ ይፋ እንደተደረገው፣ ቀጠናው ለአየር ንብረት ለውጥ እጅግ ተጋላጭ በመሆኑ ለዚህ ችግር ሊዳረግ ችሏል፤ ስለሆነም ሀገራቱ ከወዲሁ የውኃ እጥረት ከመከሰቱ በፊት ውኃን ማቆር፣ በአግባቡ መቆጠብ እና የውኃ እጥረት ወደሚታይባቸው አካባቢዎች አስቀድሞ ማጓጓዝን የመሰሉ ጠንካራ የቅድመ መከላከልና ጥንቃቄ ሥራዎችን በፈጣኑ መጀመር እንዳለባቸው ኃላፊው በጥብቅ አሳስበዋል።
seledadotio
seledadotio
ከመጪው ሐምሌ እስከ መስከረም ዓ.ም ባሉት የክረምት ወራት በኢትዮጵያ (በተለይም በመካከለኛው፣ ሰሜንና ምስራቅ አካባቢዎች) እንዲሁም በሱዳን፣ ደቡብ ሱዳን፣ በከፊል ኬንያና ኡጋንዳ ከተለመደው በታች የዝናብ እጥረት ሊከሰት እንደሚችል የኢጋድ አደጋ መከላከል ኃላፊ ዶክተር አሕመድ አምዲሆን አስጠነቀቁ።
በኢትዮጵያ ሜቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት እና በኢጋድ የአየር ጠባይ ትንበያ ማዕከል ትብብር በተዘጋጀው 73ኛው የምስራቅ አፍሪካ የአየር ጠባይ ትንተና እና ትንበያ ጉባኤ ላይ ይፋ እንደተደረገው፣ ቀጠናው ለአየር ንብረት ለውጥ እጅግ ተጋላጭ በመሆኑ ለዚህ ችግር ሊዳረግ ችሏል፤ ስለሆነም ሀገራቱ ከወዲሁ የውኃ እጥረት ከመከሰቱ በፊት ውኃን ማቆር፣ በአግባቡ መቆጠብ እና የውኃ እጥረት ወደሚታይባቸው አካባቢዎች አስቀድሞ ማጓጓዝን የመሰሉ ጠንካራ የቅድመ መከላከልና ጥንቃቄ ሥራዎችን በፈጣኑ መጀመር እንዳለባቸው ኃላፊው በጥብቅ አሳስበዋል።
seledadotio
seledadotio
16 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) ቲክ ቶክ ከኢትዮጵያ 1,820,961 ቪዲዮዎችን ማጥፋቱን ገለፀ፡፡ የማህበራዊ ሚዲያ ተቋም የሆነው ቲክ ቶክ የ2025 አራተኛ ሩብ አመት ሪፖርቱን ይፋ ያደረገ ሲሆን በዚህም ደንብ በመተላለፍ ያጠፋቸውን ቪዲዮዎች ብዛት ገልጿል፡፡ በመላው አለም ከኦክቶበር ወር እስከ ዲሴምበር ወር ድረስ ከ175 ሚሊዮን በላይ ቪዲዮዎችን ማጥፋቱን የጠቀሰው ቲክ ቶክ ከዚህ ውስጥ 1,820,961 ያህሉ የኢትዮጵያዊያን መሆኑን አስታውቋል፡፡
ከዚህ ቀደም ይፋ ባደረገው የ3ተኛው ሩብ አመት ሪፖርት ላይ ከኢትዮጵያ ከ3 ሚሊዮን በላይ ቪዲዮዎችን ማጥፋቱን ማስታወቁ የሚታወስ ነው፡፡ ዛሬ ይፋ በሆነው የ4ተኛው ሩብ አመት ሪፖርቱ ከፍተኛ መጠን ያለው ቪዲዮ ያጠፋው ከአሜሪካ መሆኑን ገልፆ ብዛታቸውም ከ10 ሚሊዮን እንደሚበልጥ አስረድቷል፡፡ ከኢትዮጵየ ጎረቤት አገራት መካከል ከኬንያ 820 ሺህ ቪዲዮ፣ ከሱዳን 1 ነጥብ አራት ሚሊዮንና ከሱማሊያ 973 ሺህ ቪዲዮ ማጥፋቱን ሪፖርቱ ጨምሮ ገልጿል፡፡
ከዚህ ቀደም ይፋ ባደረገው የ3ተኛው ሩብ አመት ሪፖርት ላይ ከኢትዮጵያ ከ3 ሚሊዮን በላይ ቪዲዮዎችን ማጥፋቱን ማስታወቁ የሚታወስ ነው፡፡ ዛሬ ይፋ በሆነው የ4ተኛው ሩብ አመት ሪፖርቱ ከፍተኛ መጠን ያለው ቪዲዮ ያጠፋው ከአሜሪካ መሆኑን ገልፆ ብዛታቸውም ከ10 ሚሊዮን እንደሚበልጥ አስረድቷል፡፡ ከኢትዮጵየ ጎረቤት አገራት መካከል ከኬንያ 820 ሺህ ቪዲዮ፣ ከሱዳን 1 ነጥብ አራት ሚሊዮንና ከሱማሊያ 973 ሺህ ቪዲዮ ማጥፋቱን ሪፖርቱ ጨምሮ ገልጿል፡፡
16 days ago
ዘ-ሐበሻ ዜና) የጠቅላይ ሚኒስትሩ የምሥራቅ አፍሪካ ጉዳዮች አማካሪ አቶ ጌታቸው ረዳ በሶማሌ ክልል መዲና ጅግጅጋ ከተማ ለሦስት ቀናት የተካሄደውን "የጅግጅጋ ፎረም" አጠናቀው መውጣታቸውን ተከትሎ የሰጡት አስተያየት፣ በቀጠናው ፖለቲካ እና መዋቅራዊ ለውጥ ዙሪያ አዳዲስ ጥያቄዎችን የሚያስነሳ ሆኗል።
አቶ ጌታቸው የፎረሙ አዘጋጆች በአጭር ጊዜ ጥሪ ውስጥ እንዲህ ያሉ ታዋቂ የአፍሪካ ቀንድ ተሳታፊዎችን በአንድ መድረክ ላይ ማገናኘት መቻላቸውን "ከተአምር የማይተናነስ" ሲሉ አወድሰውታል። ይሁን እንጂ ይህ አድናቆት በቀጠናው ስላለው እውነተኛ የፖለቲካ ውህደት ጥልቅ ጥያቄዎችን ይጋብዛል። የቀጠናው ሀገራት ዲፕሎማሲያዊ ውጥረት ውስጥ ባሉበት፣ የኢትዮጵያና የሶማሊያ ግንኙነት ገና መስመር ባልያዘበት እና የሱዳን ቀውስ ባልበረደበት በአሁኑ ወቅት፣ እንዲህ ያሉ የንግግር መድረኮች ከፖለቲካዊ ትዕይንት ባለፈ በቀጠናው መሬት ላይ ላለው ተጨባጭ ችግር ምን ያህል ዘላቂ መፍትሔ ያመጣሉ? የሚለው ጉዳይ አሁንም አጠራጣሪ ነው።
አማካሪው ለውይይት የተመረጡት ቀጠናዊ አጀንዳዎች በቀጣይ ዓመታት እጅግ አንገብጋቢ ሆነው እንደሚቀጥሉ የገለጹ ቢሆንም፣ የፖለቲካ ተንታኞች ግን እነዚህ መድረኮች ከተለመደው የአካዳሚክ ዲቤቶች እና የጋራ መግለጫዎች ባለፈ ወደ ተግባር የመቀየር አቅማቸው ደካማ መሆኑን ይተቻሉ።
በሌላ በኩል፣ አቶ ጌታቸው ረዳ ላለፉት 12 ዓመታት ወደ ከተማዋ ላልመጡ ሰዎች የጅግጅጋ ከተማ በአሁኑ ወቅት "ሊታወቅ በማይችል መልኩ" ሙሉ በሙሉ መቀየሯ እጅግ ግልጽ መሆኑን መስክረዋል። ይህ የመሠረተ ልማት ግንባታ እድገት የሚደነቅ ቢሆንም፣ ከከተማዋ ውጫዊ ገጽታ መለወጥ ጀርባ ያለው የሶማሌ ክልል ዘላቂ የውስጥ ሰላም፣ የኢኮኖሚ ተጠቃሚነት እና የፍትሃዊ ሀብት ክፍፍል ጥያቄዎች አሁንም በውይይት መድረኮች ጥላ ስር ተሸፍነው የሚቀጥሉ መሆናቸውን የፖለቲካ ታዛቢዎች ያነሳሉ።
አቶ ጌታቸው የፎረሙ ሁለተኛው ክፍል ከመጀመሩ በፊት በድጋሚ ወደ ከተማዋ ለመመለስ እንደሚጓጉ ቢገልጹም፣ ቀጣዩ ጉባኤ ከመድረሱ በፊት በጅግጅጋ የተነሱት "የቀጠናዊ ውህደት" ውጥኖች መሬት ላይ ወርደው በተግባር መፈተሻ ጊዜያቸው አሁን መሆኑን የፖለቲካው አየር ያሳያል።
አቶ ጌታቸው የፎረሙ አዘጋጆች በአጭር ጊዜ ጥሪ ውስጥ እንዲህ ያሉ ታዋቂ የአፍሪካ ቀንድ ተሳታፊዎችን በአንድ መድረክ ላይ ማገናኘት መቻላቸውን "ከተአምር የማይተናነስ" ሲሉ አወድሰውታል። ይሁን እንጂ ይህ አድናቆት በቀጠናው ስላለው እውነተኛ የፖለቲካ ውህደት ጥልቅ ጥያቄዎችን ይጋብዛል። የቀጠናው ሀገራት ዲፕሎማሲያዊ ውጥረት ውስጥ ባሉበት፣ የኢትዮጵያና የሶማሊያ ግንኙነት ገና መስመር ባልያዘበት እና የሱዳን ቀውስ ባልበረደበት በአሁኑ ወቅት፣ እንዲህ ያሉ የንግግር መድረኮች ከፖለቲካዊ ትዕይንት ባለፈ በቀጠናው መሬት ላይ ላለው ተጨባጭ ችግር ምን ያህል ዘላቂ መፍትሔ ያመጣሉ? የሚለው ጉዳይ አሁንም አጠራጣሪ ነው።
አማካሪው ለውይይት የተመረጡት ቀጠናዊ አጀንዳዎች በቀጣይ ዓመታት እጅግ አንገብጋቢ ሆነው እንደሚቀጥሉ የገለጹ ቢሆንም፣ የፖለቲካ ተንታኞች ግን እነዚህ መድረኮች ከተለመደው የአካዳሚክ ዲቤቶች እና የጋራ መግለጫዎች ባለፈ ወደ ተግባር የመቀየር አቅማቸው ደካማ መሆኑን ይተቻሉ።
በሌላ በኩል፣ አቶ ጌታቸው ረዳ ላለፉት 12 ዓመታት ወደ ከተማዋ ላልመጡ ሰዎች የጅግጅጋ ከተማ በአሁኑ ወቅት "ሊታወቅ በማይችል መልኩ" ሙሉ በሙሉ መቀየሯ እጅግ ግልጽ መሆኑን መስክረዋል። ይህ የመሠረተ ልማት ግንባታ እድገት የሚደነቅ ቢሆንም፣ ከከተማዋ ውጫዊ ገጽታ መለወጥ ጀርባ ያለው የሶማሌ ክልል ዘላቂ የውስጥ ሰላም፣ የኢኮኖሚ ተጠቃሚነት እና የፍትሃዊ ሀብት ክፍፍል ጥያቄዎች አሁንም በውይይት መድረኮች ጥላ ስር ተሸፍነው የሚቀጥሉ መሆናቸውን የፖለቲካ ታዛቢዎች ያነሳሉ።
አቶ ጌታቸው የፎረሙ ሁለተኛው ክፍል ከመጀመሩ በፊት በድጋሚ ወደ ከተማዋ ለመመለስ እንደሚጓጉ ቢገልጹም፣ ቀጣዩ ጉባኤ ከመድረሱ በፊት በጅግጅጋ የተነሱት "የቀጠናዊ ውህደት" ውጥኖች መሬት ላይ ወርደው በተግባር መፈተሻ ጊዜያቸው አሁን መሆኑን የፖለቲካው አየር ያሳያል።
17 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የትራምፕ አማካሪ አሜሪካ በምስራቅ አፍሪካ ላይ ያላትን አቋም በይፋ ገለፁ፡፡ የፕሬዝደንት ትራምፕ የአረብና አፍሪካ ጉዳዮች ከፍተኛ አማካሪ የሆኑት ማሳድ ብሉስ በትላንትናው እለት ከተለያዩ ሚዲያዎች ጋር ቃለምልልስ አድርገዋል፡፡ ይህንን አስመልክተው በኤክስ ገፃቸው ላይ ባሰፈሩት መልእክት ‹‹ከአልጀዚራ፣ አልአረቢያና ከስካይ ኒውስ አረቢያ ቻናሎች ጋር ቃለምልልስ በማድረጌ ደስታ ተሰምቶኛል፡፡›› በማለት ጀምረው በእነዚህ ቃለምልልሶች ያነሷቸውን ነጥቦች ዘርዝረዋል፡፡ ከ
እነዚህ ጉዳዮች መካከል በመጀመሪያ የጠቀሱት የሱዳንን ሁኔታ ሲሆን ፕሬዝደንት ትራምፕ የተባባሰው ሰብአዊ ቀውስ ለመፍታት ፍላጎት እንዳላቸው ማስረዳታቸውን ገልፀዋል፡፡ በበርሊን በተካሄደውና 22 አገራትና አለም አቀፍ ድርጅቶች በደገፉት ለሱዳን ግጭት ሰላማዊ መፍትሄ ለማምጣት በተቀረፀው ማእቀፍ ላይ አፅንኦት መስጠታቸውን የተናገሩት ማሳድ ብሉስ ጨምረውም ‹‹የሰብአዊነት ተኩስ አቁም እንዳይደረግ እንቅፋት የሚፈጥሩትንና ለሁለቱም ተፋላሚዎች ወታደራዊ ድጋፍ የሚሰጡ አካላት ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ አሳስባለሁ›› ብለዋል፡፡ ለሱዳን ዘላቂ ተኩስ አቁም እንደሚያስፈልጋትና በሱዳናዊያን መካከል ሁሉን ያሳተፈ ውይይት ተደርጎ ሰላማዊ የስልጣን ሽግግር እንዲደረግም ጠይቀዋል፡፡
ማሳድ ብሉስ በማስከተል እንደገለፁት በእነዚህ ቃለምልልሶቻቸው የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዮስን ጉብኝት አስመልክተው ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ በአሜሪካና ኢትዮጵያ የሁለትዮሽ ውይይት ላይ መሳተፋቸውን የገለፁት አማካሪው ከዚህ ጎን ለጎን በተለያየ ጉዳይ ላይ ውይይት መካሄዱን አስታውቀዋል፡፡ ከእነዚህ መካከልም በአባይ ወንዝ ላይ ሁለቱም አካላት ስምምነት ላይ እንዲደርሱ ፕሬዝደንት ትራምፕ የሚፈልጉ መሆኑ ለውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ የተገለፀላቸው መሆኑን ጠቅሰው በቀጠናው መረጋጋትን ለማስፈን ድጋፍ በመስጠት ላይ ውይይት መደረጉንም አስረድተዋል፡፡
እነዚህ ጉዳዮች መካከል በመጀመሪያ የጠቀሱት የሱዳንን ሁኔታ ሲሆን ፕሬዝደንት ትራምፕ የተባባሰው ሰብአዊ ቀውስ ለመፍታት ፍላጎት እንዳላቸው ማስረዳታቸውን ገልፀዋል፡፡ በበርሊን በተካሄደውና 22 አገራትና አለም አቀፍ ድርጅቶች በደገፉት ለሱዳን ግጭት ሰላማዊ መፍትሄ ለማምጣት በተቀረፀው ማእቀፍ ላይ አፅንኦት መስጠታቸውን የተናገሩት ማሳድ ብሉስ ጨምረውም ‹‹የሰብአዊነት ተኩስ አቁም እንዳይደረግ እንቅፋት የሚፈጥሩትንና ለሁለቱም ተፋላሚዎች ወታደራዊ ድጋፍ የሚሰጡ አካላት ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ አሳስባለሁ›› ብለዋል፡፡ ለሱዳን ዘላቂ ተኩስ አቁም እንደሚያስፈልጋትና በሱዳናዊያን መካከል ሁሉን ያሳተፈ ውይይት ተደርጎ ሰላማዊ የስልጣን ሽግግር እንዲደረግም ጠይቀዋል፡፡
ማሳድ ብሉስ በማስከተል እንደገለፁት በእነዚህ ቃለምልልሶቻቸው የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዮስን ጉብኝት አስመልክተው ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ በአሜሪካና ኢትዮጵያ የሁለትዮሽ ውይይት ላይ መሳተፋቸውን የገለፁት አማካሪው ከዚህ ጎን ለጎን በተለያየ ጉዳይ ላይ ውይይት መካሄዱን አስታውቀዋል፡፡ ከእነዚህ መካከልም በአባይ ወንዝ ላይ ሁለቱም አካላት ስምምነት ላይ እንዲደርሱ ፕሬዝደንት ትራምፕ የሚፈልጉ መሆኑ ለውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ የተገለፀላቸው መሆኑን ጠቅሰው በቀጠናው መረጋጋትን ለማስፈን ድጋፍ በመስጠት ላይ ውይይት መደረጉንም አስረድተዋል፡፡
17 days ago
ተፈጸመ 💔
#ethiopia | የአቶ ቢንያም ጣዕመ ሥርዓተ ቀብር ዛሬ ከቀኑ 9:00 ሰዓት ላይ በየካ ደብረ ሳህል ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን ተፈጽሟል።
💔 የአቶ ቢንያም ጣዕመ
አጭር የሕይወት ታሪክ
ሚያዚያ 13 ቀን 1969ዓም በአዲስ አበባ ከተማ ከአባቱ ከአቶ ጣዕመ ኃይሌና ከእናቱ ከወይዘሮ እግዚሃሪያ በርሔ ተወለደ።
የአንደኛና የሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱን በትውልድ ከተማው ካጠናቀቀ በኋላ ወደ ውጭ አገራት በማምራት በሱዳንና በጣሊያን በተለያዩ የሥራ ዘርፎች ተሰማርቶ ቆይቷል።
በመጨረሻም የመኖሪያ አድራሻውን በጀርመን አገር አድርጎ ይኖር ነበር።
አቶ ቢንያም በትዳር ሕይወቱ ውስጥ የአንድ ወንድና የአንድ ሴት ልጅ አባት በመሆን መልካም ቤተሰብ መሥርቷል።
በሕይወት ዘመኑ ሁሉ እጅግ ቅን፣ ተግባቢና የተከበረ ሰብዕና የነበረው በመሆኑ በዙሪያው ባሉ ሰዎች ዘንድ እጅግ ይወደድ ነበር።
ይህ ውድ ወንድማችን ግንቦት 3 ቀን 2018 ዓ.ም በድንገተኛ ሕመም ምክንያት ከዚህ ዓለም ተለይቶኗል።
ፈጣሪ አምላክ የወንድማችንን የአቶ ቢንያም ጣዕመ ነፍስ በአጸደ ገነት ያኑርልን። ለቤተሰቦቹና ለወዳጅ ዘመዶቹም መጽናናትን ይስጥልን።💔
#የቀብርሥነሥርዓት #ሀዘን #ጀርመን #የካደብረሳህል #አዲስአበባ #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | የአቶ ቢንያም ጣዕመ ሥርዓተ ቀብር ዛሬ ከቀኑ 9:00 ሰዓት ላይ በየካ ደብረ ሳህል ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን ተፈጽሟል።
💔 የአቶ ቢንያም ጣዕመ
አጭር የሕይወት ታሪክ
ሚያዚያ 13 ቀን 1969ዓም በአዲስ አበባ ከተማ ከአባቱ ከአቶ ጣዕመ ኃይሌና ከእናቱ ከወይዘሮ እግዚሃሪያ በርሔ ተወለደ።
የአንደኛና የሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱን በትውልድ ከተማው ካጠናቀቀ በኋላ ወደ ውጭ አገራት በማምራት በሱዳንና በጣሊያን በተለያዩ የሥራ ዘርፎች ተሰማርቶ ቆይቷል።
በመጨረሻም የመኖሪያ አድራሻውን በጀርመን አገር አድርጎ ይኖር ነበር።
አቶ ቢንያም በትዳር ሕይወቱ ውስጥ የአንድ ወንድና የአንድ ሴት ልጅ አባት በመሆን መልካም ቤተሰብ መሥርቷል።
በሕይወት ዘመኑ ሁሉ እጅግ ቅን፣ ተግባቢና የተከበረ ሰብዕና የነበረው በመሆኑ በዙሪያው ባሉ ሰዎች ዘንድ እጅግ ይወደድ ነበር።
ይህ ውድ ወንድማችን ግንቦት 3 ቀን 2018 ዓ.ም በድንገተኛ ሕመም ምክንያት ከዚህ ዓለም ተለይቶኗል።
ፈጣሪ አምላክ የወንድማችንን የአቶ ቢንያም ጣዕመ ነፍስ በአጸደ ገነት ያኑርልን። ለቤተሰቦቹና ለወዳጅ ዘመዶቹም መጽናናትን ይስጥልን።💔
#የቀብርሥነሥርዓት #ሀዘን #ጀርመን #የካደብረሳህል #አዲስአበባ #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
Sponsored by
Surafel
18 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) ዓለም አቀፉ የችግር አፈታት ተቋም በድረ-ገጹ ባወጣው አዲስ የትንታኔ ሪፖርት፣ አሜሪካ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ግንኙነት ለማጠናከር ከፍተኛ ጥረት እያደረገች መሆኑን አስታውቋል። ተቋሙ እንዳስነበበው፣ የአሜሪካ ኩባንያዎች በአዲስ አበባ አቅራቢያ በሚገነባው ግዙፍ የዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ እና በሌሎችም ፕሮጀክቶች ላይ መዋዕለ ንዋያቸውን እንዲያፈሱ ማበረታታቷ የዚሁ ጥረት አካል ነው። በተለይም ግንቦት 3 አሜሪካ ወደ ኢትዮጵያ የሚደረገውን የጦር መሳሪያ ሽያጭ የሚከለክለውን ፖሊሲዋን እንደምታላላ ይፋ ማድረጓን ሪፖርቱ በዋቢነት ጠቅሷል።
ክራይስስ ግሩፕ በዘገባው እንዳመለከተው፣ የአሜሪካ ባለስልጣናት የኢትዮጵያ መንግስት ከኤርትራ ጋር አዲስ ሰፊ ጦርነት የሚከፍት ከሆነ ከዋሽንግተን ጋር እያደገ የመጣው ግንኙነቱ ከባድ አደጋ ላይ እንደሚወድቅ በሚገባ እንደተረዳ ያምናሉ። ምንም እንኳን ይህ ሁኔታ በትግራይ ጉዳይ ላይም በተመሳሳይ መልኩ ተፈጻሚ መሆን አለመሆኑ ሙሉ በሙሉ ግልጽ ባይሆንም፣ ዋሽንግተን ግን አዲስ አበባ ከገባችበት የፖለቲካ ውጥረት በሰላማዊ መንገድ እንድትወጣ ለማግባባት ያላትን የዲፕሎማሲ ተጽዕኖ ፈጣሪነት በአግባቡ ልትጠቀምበት እንደሚገባ ተቋሙ አሳስቧል።
በአካባቢው እና በቀጠናው ካለው ውስብስብ ተለዋዋጭ ሁኔታ አንጻር የሰላም ሂደቱ በአጭር ጊዜ ውስጥ ተጨባጭ ለውጥ ያመጣል ብሎ ማሰብ አዳጋች መሆኑን የገለጸው ሪፖርቱ፣ የውጭ ተዋንያን ቀዳሚ ትኩረት መሆን ያለበት የፖለቲካ ውጥረቱ ተባብሶ ወደ ሌላ ጦርነት እንዳያመራ መከላከል ላይ መሆኑን አስገንዝቧል። ለዚህም ሁለቱን ወገኖች በአካልም ሆነ በአስታራቂዎች በኩል ወደ ድርድር ጠረጴዛ እንዲመጡ ማግባባት ወሳኝ የመነሻ ነጥብ ይሆናል። ከዚህም ባሻገር ሰፋ ያለ የቀጠናው የውጥረት ማስተንፈሻ እርምጃዎች እጅግ አስፈላጊ መሆናቸውን የጠቀሰው ክራይስስ ግሩፕ፣ በተለይም በአዲስ አበባ እና በሱዳን ጦር መካከል 'ለተኪ ታጣቂዎች ድጋፍ ታደርጋላችሁ' በሚል የጋራ ጥርጣሬ እያደገ የመጣውን ፍጥጫ ማርገብ ጊዜ የማይሰጠው ጉዳይ መሆኑን አብራርቷል።
የአፋጣኝ ግጭት ስጋቱ አንዴ ጋብ ካለ በኋላ፣ አዲስ አበባ እና መቀሌ የፕሪቶሪያውን የሰላም ስምምነት የሚያጠናክር እና አሁን ለተፈጠረው ከፍተኛ አለመግባባት መፍትሔ የሚያመጣ አዲስ ስምምነት ላይ መድረስ እንደሚኖርባቸው ክራይስስ ግሩፕ አጽንኦት ሰጥቷል። የተቋሙ ትንታኔ እንደሚያስረዳው፣ የማንኛውም አዲስ ስምምነት መሠረት መሆን ያለበት "አንደኛው ወገን ሌላኛውን በቀላሉ ሊያጠፋው አይችልም" የሚለውን መራር እውነት መቀበል ሲሆን፣ ይህንን በጦርነት ለማሳካት መሞከር የሚያስከትለው ኪሳራ እጅግ ግዙፍ እና አደገኛ ነው።
ትግራይ ወደ ኢትዮጵያ የፖለቲካ ፌዴሬሽን ሥርዓት እንዴት በድጋሚ ልትቀላቀል እንደምትችል የሚያሳይ ግልጽ እቅድ መኖር እንዳለበት የገለጸው ሪፖርቱ፣ በእነዚህ መሠረታዊ ጉዳዮች ላይ ጠንካራ ትኩረት ሰጥቶ መሥራት ካልተቻለ መቀሌ እና አዲስ አበባ እራሳቸውን ደጋግመው አሁን ወዳሉበት የግጭት እና የጥፋት አዙሪት ውስጥ መመለሳቸው አይቀሬ መሆኑን በማስጠንቀቅ ዘገባውን አጠናቋል።
ክራይስስ ግሩፕ በዘገባው እንዳመለከተው፣ የአሜሪካ ባለስልጣናት የኢትዮጵያ መንግስት ከኤርትራ ጋር አዲስ ሰፊ ጦርነት የሚከፍት ከሆነ ከዋሽንግተን ጋር እያደገ የመጣው ግንኙነቱ ከባድ አደጋ ላይ እንደሚወድቅ በሚገባ እንደተረዳ ያምናሉ። ምንም እንኳን ይህ ሁኔታ በትግራይ ጉዳይ ላይም በተመሳሳይ መልኩ ተፈጻሚ መሆን አለመሆኑ ሙሉ በሙሉ ግልጽ ባይሆንም፣ ዋሽንግተን ግን አዲስ አበባ ከገባችበት የፖለቲካ ውጥረት በሰላማዊ መንገድ እንድትወጣ ለማግባባት ያላትን የዲፕሎማሲ ተጽዕኖ ፈጣሪነት በአግባቡ ልትጠቀምበት እንደሚገባ ተቋሙ አሳስቧል።
በአካባቢው እና በቀጠናው ካለው ውስብስብ ተለዋዋጭ ሁኔታ አንጻር የሰላም ሂደቱ በአጭር ጊዜ ውስጥ ተጨባጭ ለውጥ ያመጣል ብሎ ማሰብ አዳጋች መሆኑን የገለጸው ሪፖርቱ፣ የውጭ ተዋንያን ቀዳሚ ትኩረት መሆን ያለበት የፖለቲካ ውጥረቱ ተባብሶ ወደ ሌላ ጦርነት እንዳያመራ መከላከል ላይ መሆኑን አስገንዝቧል። ለዚህም ሁለቱን ወገኖች በአካልም ሆነ በአስታራቂዎች በኩል ወደ ድርድር ጠረጴዛ እንዲመጡ ማግባባት ወሳኝ የመነሻ ነጥብ ይሆናል። ከዚህም ባሻገር ሰፋ ያለ የቀጠናው የውጥረት ማስተንፈሻ እርምጃዎች እጅግ አስፈላጊ መሆናቸውን የጠቀሰው ክራይስስ ግሩፕ፣ በተለይም በአዲስ አበባ እና በሱዳን ጦር መካከል 'ለተኪ ታጣቂዎች ድጋፍ ታደርጋላችሁ' በሚል የጋራ ጥርጣሬ እያደገ የመጣውን ፍጥጫ ማርገብ ጊዜ የማይሰጠው ጉዳይ መሆኑን አብራርቷል።
የአፋጣኝ ግጭት ስጋቱ አንዴ ጋብ ካለ በኋላ፣ አዲስ አበባ እና መቀሌ የፕሪቶሪያውን የሰላም ስምምነት የሚያጠናክር እና አሁን ለተፈጠረው ከፍተኛ አለመግባባት መፍትሔ የሚያመጣ አዲስ ስምምነት ላይ መድረስ እንደሚኖርባቸው ክራይስስ ግሩፕ አጽንኦት ሰጥቷል። የተቋሙ ትንታኔ እንደሚያስረዳው፣ የማንኛውም አዲስ ስምምነት መሠረት መሆን ያለበት "አንደኛው ወገን ሌላኛውን በቀላሉ ሊያጠፋው አይችልም" የሚለውን መራር እውነት መቀበል ሲሆን፣ ይህንን በጦርነት ለማሳካት መሞከር የሚያስከትለው ኪሳራ እጅግ ግዙፍ እና አደገኛ ነው።
ትግራይ ወደ ኢትዮጵያ የፖለቲካ ፌዴሬሽን ሥርዓት እንዴት በድጋሚ ልትቀላቀል እንደምትችል የሚያሳይ ግልጽ እቅድ መኖር እንዳለበት የገለጸው ሪፖርቱ፣ በእነዚህ መሠረታዊ ጉዳዮች ላይ ጠንካራ ትኩረት ሰጥቶ መሥራት ካልተቻለ መቀሌ እና አዲስ አበባ እራሳቸውን ደጋግመው አሁን ወዳሉበት የግጭት እና የጥፋት አዙሪት ውስጥ መመለሳቸው አይቀሬ መሆኑን በማስጠንቀቅ ዘገባውን አጠናቋል።
19 days ago
የኢቦላ ወረርሽኝ በድጋሚ ተቀሰቀሰ
#ethiopia | የአፍሪካ በሽታ መከላከያና መቆጣጠሪያ ማዕከል በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ምስራቃዊ ክፍል በሚገኘው ኢቱሪ በተባለው አካባቢ የኢቦላ ወረርሽኝ በድጋሚ መቀስቀሱን አስታውቋል።
ማዕከሉ ባወጣው መረጃ መሰረት እስካሁን ድረስ 246 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው የተረጋገጠ ሲሆን፣ የ65 ሰዎች ህይወት ደግሞ ለህልፈት ተዳርጓል። አብዛኛዎቹ ሟቾች ወርቅ ማውጫ በሆኑት ሞንግዋሉ እና ርዋምፓራ በተሰኙ መለስተኛ ከተሞች የተመዘገቡ መሆናቸውን የቢቢሲ ዘገባ አመላክቷል።
ቫይረሱ ከሰው ወደ ሰው በሰውነት ንክኪ እና በተጎዳ ቆዳ በሚገባ የሰውነት ፈሳሽ የሚተላለፍ ሲሆን፣ በበሽታው የተያዘ ሰው የመሞት እድሉ 50 በመቶ መሆኑን የዓለም ጤና ድርጅት ገልጿል።
ወረርሽኙን ለመግታትም የአፍሪካ በሽታ መከላከያና መቆጣጠሪያ ማዕከል ከኮንጎ፣ ርዋንዳ፣ ደቡብ ሱዳን እና ከሌሎች ዓለም አቀፍ አጋር አካላት ጋር አስቸኳይ ምክክር ለማድረግ እየተዘጋጀ ይገኛል።
ይህ አደገኛ ወረርሽኝ በፈረንጆቹ 1976 ከተገኘበት ጊዜ ጀምሮ በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ሲከሰት የአሁኑ ለ17ኛ ጊዜ መሆኑ ተመዝግቧል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን) #getutemesgen #getu
#ኢቦላ #ኮንጎ #የጤናወረርሽኝ #አፍሪካ #የአፍሪካበሽታመከላከያ #የአለምጤናድርጅት
#ethiopia | የአፍሪካ በሽታ መከላከያና መቆጣጠሪያ ማዕከል በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ምስራቃዊ ክፍል በሚገኘው ኢቱሪ በተባለው አካባቢ የኢቦላ ወረርሽኝ በድጋሚ መቀስቀሱን አስታውቋል።
ማዕከሉ ባወጣው መረጃ መሰረት እስካሁን ድረስ 246 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው የተረጋገጠ ሲሆን፣ የ65 ሰዎች ህይወት ደግሞ ለህልፈት ተዳርጓል። አብዛኛዎቹ ሟቾች ወርቅ ማውጫ በሆኑት ሞንግዋሉ እና ርዋምፓራ በተሰኙ መለስተኛ ከተሞች የተመዘገቡ መሆናቸውን የቢቢሲ ዘገባ አመላክቷል።
ቫይረሱ ከሰው ወደ ሰው በሰውነት ንክኪ እና በተጎዳ ቆዳ በሚገባ የሰውነት ፈሳሽ የሚተላለፍ ሲሆን፣ በበሽታው የተያዘ ሰው የመሞት እድሉ 50 በመቶ መሆኑን የዓለም ጤና ድርጅት ገልጿል።
ወረርሽኙን ለመግታትም የአፍሪካ በሽታ መከላከያና መቆጣጠሪያ ማዕከል ከኮንጎ፣ ርዋንዳ፣ ደቡብ ሱዳን እና ከሌሎች ዓለም አቀፍ አጋር አካላት ጋር አስቸኳይ ምክክር ለማድረግ እየተዘጋጀ ይገኛል።
ይህ አደገኛ ወረርሽኝ በፈረንጆቹ 1976 ከተገኘበት ጊዜ ጀምሮ በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ሲከሰት የአሁኑ ለ17ኛ ጊዜ መሆኑ ተመዝግቧል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን) #getutemesgen #getu
#ኢቦላ #ኮንጎ #የጤናወረርሽኝ #አፍሪካ #የአፍሪካበሽታመከላከያ #የአለምጤናድርጅት
20 days ago
ኢቦላ በኮንጎ ዳግም ተቀሰቀሰ
በዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ምስራቃዊ ክፍል በኢቦላ ወረርሽኝ ሳቢያ 65 ሰዎች ለህልፈት መዳረጋቸውን የአፍሪካ በሽታ መከላከያና መቆጣጠሪያ ማዕከል አስታወቀ።
ኢቱሪ በተባለው የአገሪቱ ክፍል ወረርሽኙ መቀስቀሱን ማዕከሉ ገልጿል።
በዚህ ሳቢያም ወደ 246 ሰዎች በወረርሽኙ መያዛቸውን ሲገልጽ 65 ሰዎች ደግሞ ለህልፈት ተዳርገዋል ብሏል።
አብዛኛዎቹ ሟቾች ወርቅ በሚወጣባቸው ሞንግዋሉ እና ርዋምፓራ በተሰኙ መለስተኛ ከተሞች የተገኙ መሆኑንን የቢቢሲ ዘገባ ያመላክታል።
አሁን ላይም ከኮንጎ፣ ርዋንዳ፣ ደቡብ ሱዳን እና ከሌሎች ዓለም አቀፍ አጋር አካላት ጋር በጉዳዩ ላይ ልመክር ነው ብሏል።
በፈረንጆቹ 1976 የተገኘው ኢቦላ በአገሪቱ ሲከሰት የአሁኑ ለ17ኛ ጊዜ መሆኑን ዘገባው አስታውሷል።
ቫይረሱ በሰውነት ንክኪ እንዲሁም በተጎዳ ቆዳ በሚገባ የሰውነት ፈሳሽ ከሰው ወደ ሰው የሚተላለፍና አደገኛ ገዳይ መሆኑ ይነገራል።
እስካሁን ክትባት አልተገኘለትም በሚባለው በዚህ ቫይረስ የተያዘ ሰው የመሞት እድሉ 50 በመቶ መሆኑን የዓለም ጤና ድርጅት መረጃ ያመላክታል።
seledadotio
seledadotio
በዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ምስራቃዊ ክፍል በኢቦላ ወረርሽኝ ሳቢያ 65 ሰዎች ለህልፈት መዳረጋቸውን የአፍሪካ በሽታ መከላከያና መቆጣጠሪያ ማዕከል አስታወቀ።
ኢቱሪ በተባለው የአገሪቱ ክፍል ወረርሽኙ መቀስቀሱን ማዕከሉ ገልጿል።
በዚህ ሳቢያም ወደ 246 ሰዎች በወረርሽኙ መያዛቸውን ሲገልጽ 65 ሰዎች ደግሞ ለህልፈት ተዳርገዋል ብሏል።
አብዛኛዎቹ ሟቾች ወርቅ በሚወጣባቸው ሞንግዋሉ እና ርዋምፓራ በተሰኙ መለስተኛ ከተሞች የተገኙ መሆኑንን የቢቢሲ ዘገባ ያመላክታል።
አሁን ላይም ከኮንጎ፣ ርዋንዳ፣ ደቡብ ሱዳን እና ከሌሎች ዓለም አቀፍ አጋር አካላት ጋር በጉዳዩ ላይ ልመክር ነው ብሏል።
በፈረንጆቹ 1976 የተገኘው ኢቦላ በአገሪቱ ሲከሰት የአሁኑ ለ17ኛ ጊዜ መሆኑን ዘገባው አስታውሷል።
ቫይረሱ በሰውነት ንክኪ እንዲሁም በተጎዳ ቆዳ በሚገባ የሰውነት ፈሳሽ ከሰው ወደ ሰው የሚተላለፍና አደገኛ ገዳይ መሆኑ ይነገራል።
እስካሁን ክትባት አልተገኘለትም በሚባለው በዚህ ቫይረስ የተያዘ ሰው የመሞት እድሉ 50 በመቶ መሆኑን የዓለም ጤና ድርጅት መረጃ ያመላክታል።
seledadotio
seledadotio
21 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) ከሱዳን ጋር በሚዋሰነው የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል፣ አሶሳ ዞን ኩምሩክ ወረዳ ውስጥ በሚገኘው የኩምሩክ ከተማ በተፈጸመ የድሮን ጥቃት፣ የዓለም አቀፉ የስደተኞች ድርጅት (IOM) ሰራተኛን ጨምሮ ቢያንስ ስምንት ንጹሃን ዜጎች መገደላቸውን እና በርካቶች መቁሰላቸውን የአካባቢው ነዋሪዎች እና የጤና ባለሙያዎች አስታወቁ። ይህ አሳዛኝ ክስተት የሱዳን የእርስ በርስ ጦርነት ድንበር ተሻግሮ በኢትዮጵያውያን ላይ ቀጥተኛ አደጋ መደቀኑን በግልጽ ያሳየ ሆኗል።
ጥቃቱ የተፈጸመው ሚያዝያ 21 ቀን 2018 ዓ.ም (እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር ኤፕሪል 29 ቀን 2026) ከጠዋቱ 5፡00 ሰዓት አካባቢ ሲሆን፣ ከአሶሳ ከተማ 94 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በምትገኘው ኩምሩክ ከተማ ውስጥ ሰዎች በብዛት በሚሰበሰቡባቸው የቡና መጠጫ እና የንግድ ስፍራዎች ላይ መሆኑ ተገልጿል። አይን እማኞች ድሮኗ የመጣችው ከሱዳን ብሉ ናይል ግዛት አቅጣጫ መሆኑን ጠቁመው፣ የሱዳን ጦር ከፈጣን ድጋፍ ሰጪ ኃይሎች (RSF) ጋር እያደረገ ባለው ጦርነት ሰበብ ይህንን ጥቃት መፈጸሙን ከሰዋል። አንድ የአካባቢው ነዋሪ ለ'አዲስ ስታንዳርድ' እንደገለጹት፣ የሱዳን ጦር የRSF ታጣቂዎች ወደ ድንበሩ ገብተዋል በሚል ጥርጣሬ በንጹሃን ላይ ጥቃት ያካሄደ ሲሆን፣ በዚህም 13 እና ከዚያ በላይ ሰዎች ህይወታቸውን አጥተዋል ብለዋል።
ከአደጋው ስፍራ ሰባት ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በሚገኘው የሆራዛብ ጤና ጣቢያ የመጀመሪያ ህክምና እርዳታ ለመስጠት ሲጥሩ የነበሩ አንድ የጤና ባለሙያ፣ አደጋውን ተከትሎ የነበረውን አስደንጋጭ ትእይንት አብራርተዋል። እግራቸው የተቆረጠ ወጣት ሴትን ጨምሮ እጅግ አሳሳቢ የሆኑ ጉዳተኞች ወደ ተቋሙ የገቡ ሲሆን፣ ሁኔታው ከአቅም በላይ በመሆኑ በዓለም አቀፉ የቀይ መስቀል ኮሚቴ ተሽከርካሪዎች እና በአምቡላንሶች ታግዘው ወደ ደሴ ሆስፒታል የተላኩም አሉ። ህክምና ጣቢያው ከደረሱት መካከል አንዲት የህክምና ባለሙያ ወዲያውኑ ህይወቷ ሲያልፍ፣ ሌላኛዋ ሴት ደግሞ እግሯ ተቆርጦ በህይወት መትረፍ ችላለች። አምስት አስከሬኖች ወደ ጤና ጣቢያው የመጡ ሲሆን፣ ሁለቱ በቤተሰብ ሲለዩ ቀሪዎቹ ማንነታቸው ሳይታወቅ ለመቀበር ተገደዋል። በጥቃቱ ህይወታቸውን ካጡት መካከል አምስት ወንዶች፣ ሁለት ሴቶች እና በከፍተኛ ደም መፍሰስ ህይወቱ ያለፈ አንድ ህጻን ልጅ ይገኙበታል።
ከሟቾቹ አንዱ በዓለም አቀፉ የስደተኞች ድርጅት (IOM) የአእምሮ ጤና እና የስነ-ልቦና ድጋፍ ሰጪ ባለሙያ መሆኑን ነዋሪዎች ተናግረዋል። ሌላ ተጨማሪ የድርጅቱ ሰራተኛ ደግሞ እግሩን እስከማጣት የደረሰ ከባድ ጉዳት ደርሶበት በአሶሳ ህክምና እየተከታተለ ይገኛል። ከዚህም ባሻገር፣ ነዋሪዎቹ የRSF ታጣቂዎች የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት የደንብ ልብስ ለብሰው በድንበር አካባቢ በሚገኙ ቀበሌዎች ውስጥ በመንቀሳቀስ በንጹሃን ላይ ዘረፋ፣ ማስፈራራት እና ጾታዊ ጥቃት እየፈጸሙ መሆኑን አጋልጠዋል። እነዚህ ታጣቂዎች ያለክፍያ በመብላትና በመጠጣት "አብይ ይክፈላችሁ" በማለት ነዋሪውን እንደሚያንገላቱ አንድ የአካባቢው ሰው በምሬት ገልጸው፣ በአካባቢው ባለው የጸጥታ ችግር ምክንያት ለቆሰሉ ሰዎች እርዳታ ማድረስ ፈታኝ እንደሆነ አክለዋል።
ይህ በኢትዮጵያ ግዛት ውስጥ የተፈጸመው ጥቃት፣ በሁለቱ ሀገራት ድንበር ላይ እየተባባሰ የመጣውን ውጥረት ተከትሎ የተከሰተ ነው። በቅርቡ የሱዳን ጦር ከቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ጋር በሚዋሰነው የብሉ ናይል ግዛት እንዲሁም በአማራ ክልል ድንበር አል-ፋሻጋ አካባቢ ተጨማሪ ጦር እና ፀረ-አውሮፕላን መከላከያዎችን አስፍሯል። የሱዳን ባለስልጣናት ኢትዮጵያ እና የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች በካርቱም አውሮፕላን ማረፊያ እና ሌሎች ስትራቴጂካዊ ስፍራዎች ላይ የድሮን ጥቃት ፈጽመዋል በሚል ሲከሱ ቆይተዋል። የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ክሱን "መሰረተ ቢስ" በማለት ውድቅ ያደረገው ሲሆን፣ የሁለቱን ሀገራት ታሪካዊ ወዳጅነት በማስታወስ በሱዳን ያለው የእርስ በርስ ጦርነት እንዲረግብ ጥሪ ማቅረቡ ይታወሳል።
የሱዳን ባለስልጣናት ኢትዮጵያ ለRSF ድጋፍ ታደርጋለች የሚለውን ክስ በተደጋጋሚ የሚያነሱ ሲሆን፣ ኢትዮጵያ ይህንን ክስ አጥብቃ ትቃወማለች። ይህ ውንጀላ ባለፈው መጋቢት ወር ሱዳን አምባሳደሯን ከኢትዮጵያ እስከመጥራት አድርሷታል። ይሁን እንጂ ሂዩማን ራይትስ ላብ የተባለ ተቋም የሳተላይት ምስሎችን ዋቢ አድርጎ በቅርቡ ባወጣው ሪፖርት፣ በአሶሳ አቅራቢያ ከሚገኝ የኢትዮጵያ ግዛት ውስጥ ለRSF እንቅስቃሴ ድጋፍ እንደሚሰጥ ጠቁሟል። ምንም እንኳን በኢትዮጵያ ግዛት ውስጥ የጸጥታ መደፍረሱ እያደገ ቢመጣም እና የንጹሃን ህይወት በድሮን ጥቃት ቢያልፍም፣ የኢትዮጵያ መንግስት በኩምሩኩ ክስተት ዙሪያ እስካሁን ይፋዊ ምላሽ አለመስጠቱን የአካባቢው ነዋሪዎች በቅሬታ አንስተዋል።
ጥቃቱ የተፈጸመው ሚያዝያ 21 ቀን 2018 ዓ.ም (እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር ኤፕሪል 29 ቀን 2026) ከጠዋቱ 5፡00 ሰዓት አካባቢ ሲሆን፣ ከአሶሳ ከተማ 94 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በምትገኘው ኩምሩክ ከተማ ውስጥ ሰዎች በብዛት በሚሰበሰቡባቸው የቡና መጠጫ እና የንግድ ስፍራዎች ላይ መሆኑ ተገልጿል። አይን እማኞች ድሮኗ የመጣችው ከሱዳን ብሉ ናይል ግዛት አቅጣጫ መሆኑን ጠቁመው፣ የሱዳን ጦር ከፈጣን ድጋፍ ሰጪ ኃይሎች (RSF) ጋር እያደረገ ባለው ጦርነት ሰበብ ይህንን ጥቃት መፈጸሙን ከሰዋል። አንድ የአካባቢው ነዋሪ ለ'አዲስ ስታንዳርድ' እንደገለጹት፣ የሱዳን ጦር የRSF ታጣቂዎች ወደ ድንበሩ ገብተዋል በሚል ጥርጣሬ በንጹሃን ላይ ጥቃት ያካሄደ ሲሆን፣ በዚህም 13 እና ከዚያ በላይ ሰዎች ህይወታቸውን አጥተዋል ብለዋል።
ከአደጋው ስፍራ ሰባት ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በሚገኘው የሆራዛብ ጤና ጣቢያ የመጀመሪያ ህክምና እርዳታ ለመስጠት ሲጥሩ የነበሩ አንድ የጤና ባለሙያ፣ አደጋውን ተከትሎ የነበረውን አስደንጋጭ ትእይንት አብራርተዋል። እግራቸው የተቆረጠ ወጣት ሴትን ጨምሮ እጅግ አሳሳቢ የሆኑ ጉዳተኞች ወደ ተቋሙ የገቡ ሲሆን፣ ሁኔታው ከአቅም በላይ በመሆኑ በዓለም አቀፉ የቀይ መስቀል ኮሚቴ ተሽከርካሪዎች እና በአምቡላንሶች ታግዘው ወደ ደሴ ሆስፒታል የተላኩም አሉ። ህክምና ጣቢያው ከደረሱት መካከል አንዲት የህክምና ባለሙያ ወዲያውኑ ህይወቷ ሲያልፍ፣ ሌላኛዋ ሴት ደግሞ እግሯ ተቆርጦ በህይወት መትረፍ ችላለች። አምስት አስከሬኖች ወደ ጤና ጣቢያው የመጡ ሲሆን፣ ሁለቱ በቤተሰብ ሲለዩ ቀሪዎቹ ማንነታቸው ሳይታወቅ ለመቀበር ተገደዋል። በጥቃቱ ህይወታቸውን ካጡት መካከል አምስት ወንዶች፣ ሁለት ሴቶች እና በከፍተኛ ደም መፍሰስ ህይወቱ ያለፈ አንድ ህጻን ልጅ ይገኙበታል።
ከሟቾቹ አንዱ በዓለም አቀፉ የስደተኞች ድርጅት (IOM) የአእምሮ ጤና እና የስነ-ልቦና ድጋፍ ሰጪ ባለሙያ መሆኑን ነዋሪዎች ተናግረዋል። ሌላ ተጨማሪ የድርጅቱ ሰራተኛ ደግሞ እግሩን እስከማጣት የደረሰ ከባድ ጉዳት ደርሶበት በአሶሳ ህክምና እየተከታተለ ይገኛል። ከዚህም ባሻገር፣ ነዋሪዎቹ የRSF ታጣቂዎች የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት የደንብ ልብስ ለብሰው በድንበር አካባቢ በሚገኙ ቀበሌዎች ውስጥ በመንቀሳቀስ በንጹሃን ላይ ዘረፋ፣ ማስፈራራት እና ጾታዊ ጥቃት እየፈጸሙ መሆኑን አጋልጠዋል። እነዚህ ታጣቂዎች ያለክፍያ በመብላትና በመጠጣት "አብይ ይክፈላችሁ" በማለት ነዋሪውን እንደሚያንገላቱ አንድ የአካባቢው ሰው በምሬት ገልጸው፣ በአካባቢው ባለው የጸጥታ ችግር ምክንያት ለቆሰሉ ሰዎች እርዳታ ማድረስ ፈታኝ እንደሆነ አክለዋል።
ይህ በኢትዮጵያ ግዛት ውስጥ የተፈጸመው ጥቃት፣ በሁለቱ ሀገራት ድንበር ላይ እየተባባሰ የመጣውን ውጥረት ተከትሎ የተከሰተ ነው። በቅርቡ የሱዳን ጦር ከቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ጋር በሚዋሰነው የብሉ ናይል ግዛት እንዲሁም በአማራ ክልል ድንበር አል-ፋሻጋ አካባቢ ተጨማሪ ጦር እና ፀረ-አውሮፕላን መከላከያዎችን አስፍሯል። የሱዳን ባለስልጣናት ኢትዮጵያ እና የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች በካርቱም አውሮፕላን ማረፊያ እና ሌሎች ስትራቴጂካዊ ስፍራዎች ላይ የድሮን ጥቃት ፈጽመዋል በሚል ሲከሱ ቆይተዋል። የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ክሱን "መሰረተ ቢስ" በማለት ውድቅ ያደረገው ሲሆን፣ የሁለቱን ሀገራት ታሪካዊ ወዳጅነት በማስታወስ በሱዳን ያለው የእርስ በርስ ጦርነት እንዲረግብ ጥሪ ማቅረቡ ይታወሳል።
የሱዳን ባለስልጣናት ኢትዮጵያ ለRSF ድጋፍ ታደርጋለች የሚለውን ክስ በተደጋጋሚ የሚያነሱ ሲሆን፣ ኢትዮጵያ ይህንን ክስ አጥብቃ ትቃወማለች። ይህ ውንጀላ ባለፈው መጋቢት ወር ሱዳን አምባሳደሯን ከኢትዮጵያ እስከመጥራት አድርሷታል። ይሁን እንጂ ሂዩማን ራይትስ ላብ የተባለ ተቋም የሳተላይት ምስሎችን ዋቢ አድርጎ በቅርቡ ባወጣው ሪፖርት፣ በአሶሳ አቅራቢያ ከሚገኝ የኢትዮጵያ ግዛት ውስጥ ለRSF እንቅስቃሴ ድጋፍ እንደሚሰጥ ጠቁሟል። ምንም እንኳን በኢትዮጵያ ግዛት ውስጥ የጸጥታ መደፍረሱ እያደገ ቢመጣም እና የንጹሃን ህይወት በድሮን ጥቃት ቢያልፍም፣ የኢትዮጵያ መንግስት በኩምሩኩ ክስተት ዙሪያ እስካሁን ይፋዊ ምላሽ አለመስጠቱን የአካባቢው ነዋሪዎች በቅሬታ አንስተዋል።
21 days ago
በኢትዮጵያ ኩርሙክ ከተማ ሱዳን ፈፀመችው በተባለ የድሮን ጥቃት ሰላማዊ ሰዎች ሲገደሉ በእርዳታ ሰጪዎች ላይ ጉዳት ደረሰ!
ከሱዳን ድንበር አቅራቢያ በሚገኘው በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል አሶሳ ዞን ኩርሙክ ወረዳ ኩርሙክ ከተማ ውስጥ በተፈጸመ የድሮን ጥቃት፣ አንድ የዓለም አቀፉ የስደተኞች ድርጅት (IOM) የሥራ ባልደረባን ጨምሮ ቢያንስ ስምንት ሰላማዊ ሰዎች መገደላቸውንና ሌሎች በርካታ ሰዎች መቁሰላቸውን ነዋሪዎች እና የአካባቢው የጤና ባለሥልጣናት ገለጹ።
ነዋሪዎች ጥቃቱ የተፈጸመው ሚያዝያ 21 ቀን 2018 ዓ.ም. ከቀኑ 5:00 ገደማ መሆኑንና ከአሶሳ ከተማ 94 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በምትገኘው የኩርሙክ ከተማ የሰዎች እንቅስቃሴ በሚበዛበት አካባቢ ላይ ማረፉን ተናግረዋል።የዓይን እማኞች ድሮኑ የመጣው ከሱዳን ብሉ ናይል ግዛት አቅጣጫ መሆኑን ጠቅሰው፣ የሱዳን ጦር ከፈጣን ድጋፍ ኃይሎች (RSF) ጋር እያካሄደ በነበረው ግጭት ወቅት ጥቃቱን እንደፈጸመ አስረድተዋል።
seledadotio
seledadotio
ከሱዳን ድንበር አቅራቢያ በሚገኘው በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል አሶሳ ዞን ኩርሙክ ወረዳ ኩርሙክ ከተማ ውስጥ በተፈጸመ የድሮን ጥቃት፣ አንድ የዓለም አቀፉ የስደተኞች ድርጅት (IOM) የሥራ ባልደረባን ጨምሮ ቢያንስ ስምንት ሰላማዊ ሰዎች መገደላቸውንና ሌሎች በርካታ ሰዎች መቁሰላቸውን ነዋሪዎች እና የአካባቢው የጤና ባለሥልጣናት ገለጹ።
ነዋሪዎች ጥቃቱ የተፈጸመው ሚያዝያ 21 ቀን 2018 ዓ.ም. ከቀኑ 5:00 ገደማ መሆኑንና ከአሶሳ ከተማ 94 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በምትገኘው የኩርሙክ ከተማ የሰዎች እንቅስቃሴ በሚበዛበት አካባቢ ላይ ማረፉን ተናግረዋል።የዓይን እማኞች ድሮኑ የመጣው ከሱዳን ብሉ ናይል ግዛት አቅጣጫ መሆኑን ጠቅሰው፣ የሱዳን ጦር ከፈጣን ድጋፍ ኃይሎች (RSF) ጋር እያካሄደ በነበረው ግጭት ወቅት ጥቃቱን እንደፈጸመ አስረድተዋል።
seledadotio
seledadotio
21 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የኤርትራ የማስታወቂያ ሚኒስትር አቶ የማነ ገብረመስቀል፣ የብልጽግና ፓርቲ) በአፍሪካ ቀንድ አካባቢ እየተከተላቸው ያሉ ፖሊሲዎች እና አቋሞች ቀጣናዊ ውጥረት እንዲፈጠር እያደረጉ ነው ሲሉ ከሰሱ። ሚኒስትሩ በኤክስ ማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት ጽሁፍ የኢትዮጵያን መንግስት ፖሊሲዎች "ከእውነታው የራቁ" ሲሉ ገልጸዋቸዋል።
አቶ የማነ ለክሳቸው ዋነኛ ማሳያ አድርገው ያነሱት፣ በመጀመሪያ የኢትዮጵያ መንግስት በጥር ወር 2024 (እ.ኤ.አ) ከሶማሊላንድ ጋር የተፈራረመው የመግባቢያ ስምምነት (MOU) ህገ-ወጥ እና በድብቅ የተደረገ ነው የሚል ነው። በሁለተኛ ደረጃ፣ ከታህሳስ 2023 (እ.ኤ.አ) ጀምሮ "በሉዓላዊነት ላይ የተመሰረተ የባህር በር ማግኘት" በሚል መነሻ አሰብን ለመውረር የጦር መሳሪያ ማስፈራሪያዎችን እና ተከታታይ የሚዲያና የዲፕሎማሲ ዘመቻዎችን አካሂዷል ሲሉ ተችተዋል። በሶስተኛ ደረጃ ደግሞ፣ እንደ ዬል ዩኒቨርሲቲ ጥናቶች ያሉ ሪፖርቶችን ዋቢ በማድረግ ኢትዮጵያ በሱዳን ግጭት ውስጥ እጇን አስገብታለች የሚል ክስ አቅርበዋል።
ሚኒስትሩ አክለውም የኢትዮጵያ መንግስት ደጋፊዎች "ኤርትራን እና ሌሎች የቀጠናውን ሀገራት በኢትዮጵያ ላይ ፀረ-ኢትዮጵያ ጥምረት በመፍጠር ሴራ እየጎነጎኑ ነው" በሚል የሚያነሱት ክስ ሀሰተኛ እና የውጥረቱን ትክክለኛ ምንጭ ለመሸፈን የሚደረግ ሙከራ ነው ብለዋል።
አቶ የማነ፣ የአፍሪካ ቀንድ ህዝቦች ፍላጎት "በአንዳቸው የሌላውን ሉዓላዊነት እና የግዛት አንድነት በማክበር ላይ የተመሰረተ ዘላቂ ሰላም እና ትብብር ማምጣት እንጂ፣ የበላይነትን ለማስፈን በሚደረግ ጥረት ለዘመናት በሚዘልቅ ግጭት ውስጥ መኖር አይደለም" ሲሉ የሀገራቸውን አቋም ገልጸዋል።
የኢትዮጵያ መንግስት የኤርትራው ማስታወቂያ ሚ/ር በተደጋጋሚ ለሚያቀርቡት ክስ አንድም ቀን ምላሽ ሰጥቶ አያውቅም። ለዚህም ክስ እስካሁን የሰጠው ምላሽ የለም።
አቶ የማነ ለክሳቸው ዋነኛ ማሳያ አድርገው ያነሱት፣ በመጀመሪያ የኢትዮጵያ መንግስት በጥር ወር 2024 (እ.ኤ.አ) ከሶማሊላንድ ጋር የተፈራረመው የመግባቢያ ስምምነት (MOU) ህገ-ወጥ እና በድብቅ የተደረገ ነው የሚል ነው። በሁለተኛ ደረጃ፣ ከታህሳስ 2023 (እ.ኤ.አ) ጀምሮ "በሉዓላዊነት ላይ የተመሰረተ የባህር በር ማግኘት" በሚል መነሻ አሰብን ለመውረር የጦር መሳሪያ ማስፈራሪያዎችን እና ተከታታይ የሚዲያና የዲፕሎማሲ ዘመቻዎችን አካሂዷል ሲሉ ተችተዋል። በሶስተኛ ደረጃ ደግሞ፣ እንደ ዬል ዩኒቨርሲቲ ጥናቶች ያሉ ሪፖርቶችን ዋቢ በማድረግ ኢትዮጵያ በሱዳን ግጭት ውስጥ እጇን አስገብታለች የሚል ክስ አቅርበዋል።
ሚኒስትሩ አክለውም የኢትዮጵያ መንግስት ደጋፊዎች "ኤርትራን እና ሌሎች የቀጠናውን ሀገራት በኢትዮጵያ ላይ ፀረ-ኢትዮጵያ ጥምረት በመፍጠር ሴራ እየጎነጎኑ ነው" በሚል የሚያነሱት ክስ ሀሰተኛ እና የውጥረቱን ትክክለኛ ምንጭ ለመሸፈን የሚደረግ ሙከራ ነው ብለዋል።
አቶ የማነ፣ የአፍሪካ ቀንድ ህዝቦች ፍላጎት "በአንዳቸው የሌላውን ሉዓላዊነት እና የግዛት አንድነት በማክበር ላይ የተመሰረተ ዘላቂ ሰላም እና ትብብር ማምጣት እንጂ፣ የበላይነትን ለማስፈን በሚደረግ ጥረት ለዘመናት በሚዘልቅ ግጭት ውስጥ መኖር አይደለም" ሲሉ የሀገራቸውን አቋም ገልጸዋል።
የኢትዮጵያ መንግስት የኤርትራው ማስታወቂያ ሚ/ር በተደጋጋሚ ለሚያቀርቡት ክስ አንድም ቀን ምላሽ ሰጥቶ አያውቅም። ለዚህም ክስ እስካሁን የሰጠው ምላሽ የለም።
21 days ago
u1230u1260u122d - u12a0u121cu122au12ab u1260u12a2u1275u12eeu1335u12eb u120bu12ed u1260u12c8u1230u1290u127du12cd u12cdu1233u1294 u1231u12f3u1295 u1260u1241u1323 u1308u1295u134du120bu1208u127d! ud83dude31 #ethiopia #sudan #usforeignpolicy #hornofafrica #geopolitics ","delight_ranges":[],"image_ranges":[],"inline_style_ranges":[],"aggregated_ranges":[],"ranges":[{"entity":{"__typename":"Hashtag","__isEntity":"Hashtag","url":"https://www.facebook.com/h...
ሰበር - አሜሪካ በኢትዮጵያ ላይ በወሰነችው ውሳኔ ሱዳን በቁጣ ገንፍላለች! 😱 #ethiopia #sudan #usforeignpolicy #hornofafrica #geopolitics
Sponsored by
Surafel
21 days ago
ሰበር - አሜሪካ በኢትዮጵያ ላይ በወሰነችው ውሳኔ ሱዳን በቁጣ ገንፍላለች! 😱 #ethiopia #sudan #usforeignpolicy #hornofafrica #geopolitics
ሰበር - አሜሪካ በኢትዮጵያ ላይ በወሰነችው ውሳኔ ሱዳን በቁጣ ገንፍላለች! 😱 #ethiopia #sudan #usforeignpolicy #hornofafrica #geopolitics
22 days ago
#ስደተኞች
በየቀኑ 1,000 የሚደርሱ የደቡብ ሱዳን ዜጎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚሰደዱ ተመላከተ።
ተመድ ባወጣው አዲስ ሪፖርት ከእነዚህ ስደተኞች 95% የሚሆኑት ሴቶች እና ህፃናት መሆናቸውን ገልጿል።
የተመድ ስደተኞች ኤጀንሲ ቃል አቀባይ መሊሳ ፍሌሚንግ በጄኔቭ በሰጡት መግለጫ ወደኢትዮጵያ በሚሰደዱበት ወቅት ሴቶችም ሆኑ ወንዶች በግዳጅ ለጦርነት እንደሚመለመሉም ተናግረዋል።
በዚህም፣ ፍቃደኛ ያልሆኑ በመንገድ ላይ እያሉ በመልማይ ታጣቂዎች ኢላማ ተደርገው ግድያ እንደሚፈፀምባቸውም አብራርተዋል።
የተመድ የስደተኞች ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ከመጋቢት 2026 ጀምሮ ብቻ ከ100 ሺሕ የሚልቁ የደቡብ ሱዳን ዜጎች ወደ ኢትዮጵያ ተሰደው ገብተዋል።
Via.un news
seledadotio
seledadotio
በየቀኑ 1,000 የሚደርሱ የደቡብ ሱዳን ዜጎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚሰደዱ ተመላከተ።
ተመድ ባወጣው አዲስ ሪፖርት ከእነዚህ ስደተኞች 95% የሚሆኑት ሴቶች እና ህፃናት መሆናቸውን ገልጿል።
የተመድ ስደተኞች ኤጀንሲ ቃል አቀባይ መሊሳ ፍሌሚንግ በጄኔቭ በሰጡት መግለጫ ወደኢትዮጵያ በሚሰደዱበት ወቅት ሴቶችም ሆኑ ወንዶች በግዳጅ ለጦርነት እንደሚመለመሉም ተናግረዋል።
በዚህም፣ ፍቃደኛ ያልሆኑ በመንገድ ላይ እያሉ በመልማይ ታጣቂዎች ኢላማ ተደርገው ግድያ እንደሚፈፀምባቸውም አብራርተዋል።
የተመድ የስደተኞች ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ከመጋቢት 2026 ጀምሮ ብቻ ከ100 ሺሕ የሚልቁ የደቡብ ሱዳን ዜጎች ወደ ኢትዮጵያ ተሰደው ገብተዋል።
Via.un news
seledadotio
seledadotio
22 days ago
አሜሪካ በኢትዮጵያ ላይ ጥላው የነበረውን የጦር መሣሪያ ማዕቀብ አነሳች
በኢትዮጵያ ላይ ተጥሎ የነበረው የጦር መሳሪያ ማዕቀብ መነሳቱን አሜሪካ አስታወቀች። ማዕቀቡ መነሳቱን የገለፀው በአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአገር መከላከያ ንግድ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት ነው።
ዳይሬክቶሬቱ ሰኞ ግንቦት 3/2018 ዓ.ም. እንደገለጸው በኢትዮጵያ ላይ ይከተል የነበረውን የክልከላ ፖሊሲ በማንሳት አሁን ላይ በዓለም አቀፍ የጦር መሣሪያ ዝውውር ደንብ (ITAR) ቁጥጥር የሚደረግባቸውን እና ከኢትዮጵያ ጋር የተያያዙ የፈቃድ ማመልከቻዎችን በየተራ እየገመገመ ነው።
ይህን ተከትሎ በቅርቡ በሚወጣ የደንብ ለውጥ፣ ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ የጦር መሳሪያ ዝውውር ደንብ - ITAR 126.1 ዝርዝር ውስጥ ከሚገኙ አገራት ተርታ "እንድትሰረዝ" የሚደረግ መሆኑን ጠቅሷል።
ይህ ደንብ፣ በአሜሪካ ማዕቀብ ስር የሚገኙ የተወሰኑ አገራት፤ ለመከላከያ ሠራዊት፣ ለፖሊስ፣ ለደህንነት እና ለሌሎችም የአገር ውስጥ የጸጥታ ኃይሎቻቸው የሚሆኑ የመከላከያ ቁሳቁሶችን እና አገልግሎቶችን ከውጭ ገዝተው ማስገባትም ሆነ ወደ ውጭ አገራት መላክ እንዳይችሉ የሚከለክል ነው።
ኢትዮጵያ በሰሜን ኢትዮጵያ ከነበረው የትግራይ ጦርነት ጋር በተያያዘ ከኅዳር 2014 ዓ.ም. ጀምሮ ከ4 ዓመታት በላይ በዚህ ማዕቀብ ውስጥ ቆይታለች።
ኢትዮጵያ ከጥቂት ዓመታት በፊት የጦር መሣሪያ በብዛት የጦር መሣሪያ የምትገዛው ከሩሲያ፣ ቻይና፣ ቱርክ፣ የተባበሩት አረብ ኤሜሬትስ እና ኢራን መሆኑን የተለያዩ መረጃዎች ያሳያሉ።
አሜሪካ ጥላ የነበረው ማዕቀብ መነሳቱ ይፋ የሆነው በኢትዮጵያ ግጭቶች በቀጠሉበት እና የትግራይ ክልል ውጥረት ባየለበት፤ በኢትዮጵያ እና በኤርትራ እንዲሁም በኢትዮጵያ እና በሱዳን መካከል ውጥረት ባለበት ወቅት ነው።
አሜሪካ በኢትዮጵያ ላይ ጥላው የነበረውን የጦር መሳርያ ማዕቀብ ለማንሳት ከውሳኔ ላይ የደረሰችበትን ምክንያት በይፋ አልገለጸችም።
ሆኖም የአሜሪካ መከላከያ ንግድ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት ይህ ማዕቀብ መነሳቱን ይፋ ያደረገው፤ የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቴዎስ (ዶ/ር) ወደ ዋሽንግተን አቅንተው ከአሜሪካው አቻቸው ማርኮ ሩቢዮ ጋር በሁለትዮሽ እና የምሥራቅ አፍሪካ ቀጣናዊ ጉዳዮች ላይ መነጋገራቸውን ተከትሎ ነው።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮቹ በውይይታቸው፤ በምሥራቅ አፍሪካ የሚከሰቱ ግጭቶችን በመፍታት እና ውጥረቶችን በማርገብ ረገድ ኢትዮጵያ "በምትጫወተውን ወሳኝ ሚና" ላይ አጽንኦት ሰጥተው መነጋገራቸውን የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል። በተጨማሪም የሁለቱ አገራት የጸጥታ አጋርነት፣ እንዲሁም የአገራቱን የንግድ ዕድሎች ማሳደግ፤ "ቀይ ባሕር እና የማሪታይም ደኅንነት" ጉዳዮች ውይይታቸው የዳሰሷቸው ነጥቦች ናቸው።
ማርኮ ሩቢዮ ከዶ/ር ጌዲዮን ጋር በአካል ተገናኝተው ከመነጋገራቸው አስቀድሞ፤ በዚያው ዕለት ከኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ጋር በቀጠናዊ መረጋጋት፣ በጸረ-ሽብር ትብብር፣ በኢኮኖሚ እና በአፍሪካ ቀንድ ደህንነት ዙሪያ በስልክ ተወያይተዋል።
የአሜሪካ እና የኢትዮጵያ ባለሥልጣናት ቀይ ባሕርን ጨምሮ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ከመወያየታቸው እና በኢትዮጵያ ላይ ተጥሎ የነበረው የጦር መሳርያ ማዕቀብ ከመነሳቱ ጥቂት ቀናት አስቀድማ አሜሪካ በኤርትራ ላይ የጣለችውን ማዕቀብ ለማንሳት ማቀዷ መዘገቡ ይታወሳል።
ዘገባው የቢቢሲ አማርኛ ነው።
በኢትዮጵያ ላይ ተጥሎ የነበረው የጦር መሳሪያ ማዕቀብ መነሳቱን አሜሪካ አስታወቀች። ማዕቀቡ መነሳቱን የገለፀው በአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአገር መከላከያ ንግድ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት ነው።
ዳይሬክቶሬቱ ሰኞ ግንቦት 3/2018 ዓ.ም. እንደገለጸው በኢትዮጵያ ላይ ይከተል የነበረውን የክልከላ ፖሊሲ በማንሳት አሁን ላይ በዓለም አቀፍ የጦር መሣሪያ ዝውውር ደንብ (ITAR) ቁጥጥር የሚደረግባቸውን እና ከኢትዮጵያ ጋር የተያያዙ የፈቃድ ማመልከቻዎችን በየተራ እየገመገመ ነው።
ይህን ተከትሎ በቅርቡ በሚወጣ የደንብ ለውጥ፣ ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ የጦር መሳሪያ ዝውውር ደንብ - ITAR 126.1 ዝርዝር ውስጥ ከሚገኙ አገራት ተርታ "እንድትሰረዝ" የሚደረግ መሆኑን ጠቅሷል።
ይህ ደንብ፣ በአሜሪካ ማዕቀብ ስር የሚገኙ የተወሰኑ አገራት፤ ለመከላከያ ሠራዊት፣ ለፖሊስ፣ ለደህንነት እና ለሌሎችም የአገር ውስጥ የጸጥታ ኃይሎቻቸው የሚሆኑ የመከላከያ ቁሳቁሶችን እና አገልግሎቶችን ከውጭ ገዝተው ማስገባትም ሆነ ወደ ውጭ አገራት መላክ እንዳይችሉ የሚከለክል ነው።
ኢትዮጵያ በሰሜን ኢትዮጵያ ከነበረው የትግራይ ጦርነት ጋር በተያያዘ ከኅዳር 2014 ዓ.ም. ጀምሮ ከ4 ዓመታት በላይ በዚህ ማዕቀብ ውስጥ ቆይታለች።
ኢትዮጵያ ከጥቂት ዓመታት በፊት የጦር መሣሪያ በብዛት የጦር መሣሪያ የምትገዛው ከሩሲያ፣ ቻይና፣ ቱርክ፣ የተባበሩት አረብ ኤሜሬትስ እና ኢራን መሆኑን የተለያዩ መረጃዎች ያሳያሉ።
አሜሪካ ጥላ የነበረው ማዕቀብ መነሳቱ ይፋ የሆነው በኢትዮጵያ ግጭቶች በቀጠሉበት እና የትግራይ ክልል ውጥረት ባየለበት፤ በኢትዮጵያ እና በኤርትራ እንዲሁም በኢትዮጵያ እና በሱዳን መካከል ውጥረት ባለበት ወቅት ነው።
አሜሪካ በኢትዮጵያ ላይ ጥላው የነበረውን የጦር መሳርያ ማዕቀብ ለማንሳት ከውሳኔ ላይ የደረሰችበትን ምክንያት በይፋ አልገለጸችም።
ሆኖም የአሜሪካ መከላከያ ንግድ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት ይህ ማዕቀብ መነሳቱን ይፋ ያደረገው፤ የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቴዎስ (ዶ/ር) ወደ ዋሽንግተን አቅንተው ከአሜሪካው አቻቸው ማርኮ ሩቢዮ ጋር በሁለትዮሽ እና የምሥራቅ አፍሪካ ቀጣናዊ ጉዳዮች ላይ መነጋገራቸውን ተከትሎ ነው።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮቹ በውይይታቸው፤ በምሥራቅ አፍሪካ የሚከሰቱ ግጭቶችን በመፍታት እና ውጥረቶችን በማርገብ ረገድ ኢትዮጵያ "በምትጫወተውን ወሳኝ ሚና" ላይ አጽንኦት ሰጥተው መነጋገራቸውን የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል። በተጨማሪም የሁለቱ አገራት የጸጥታ አጋርነት፣ እንዲሁም የአገራቱን የንግድ ዕድሎች ማሳደግ፤ "ቀይ ባሕር እና የማሪታይም ደኅንነት" ጉዳዮች ውይይታቸው የዳሰሷቸው ነጥቦች ናቸው።
ማርኮ ሩቢዮ ከዶ/ር ጌዲዮን ጋር በአካል ተገናኝተው ከመነጋገራቸው አስቀድሞ፤ በዚያው ዕለት ከኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ጋር በቀጠናዊ መረጋጋት፣ በጸረ-ሽብር ትብብር፣ በኢኮኖሚ እና በአፍሪካ ቀንድ ደህንነት ዙሪያ በስልክ ተወያይተዋል።
የአሜሪካ እና የኢትዮጵያ ባለሥልጣናት ቀይ ባሕርን ጨምሮ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ከመወያየታቸው እና በኢትዮጵያ ላይ ተጥሎ የነበረው የጦር መሳርያ ማዕቀብ ከመነሳቱ ጥቂት ቀናት አስቀድማ አሜሪካ በኤርትራ ላይ የጣለችውን ማዕቀብ ለማንሳት ማቀዷ መዘገቡ ይታወሳል።
ዘገባው የቢቢሲ አማርኛ ነው።
23 days ago
የኢትዮጵያ እና የተመድ የ80 ዓመታት ታሪካዊ ቁርኝት
****************
በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት (ተመድ) የስምንት ዐሥርተ ዓመታት ጉዞ ውስጥ፣ ኢትዮጵያ በጋራ ደኅንነት፣ በሰላም እና በልማት ፅኑ አቋም ይዛ በዓለም አቀፍ መድረክ ደማቅ አሻራዋን አኑራለች።
ይህ ከትውልድ ወደ ትውልድ የተሻገረው የባለብዙ ወገን ዲፕሎማሲ ጉዞ ተመድ የተመሠረተበትን በዓል ሲያከብር፣ የድርጅቱ ቀዳሚ መሥራች እና ንቁ ተሳታፊ የሆነችው ሀገራችን በዓለም አቀፍ ዲፕሎማሲ፣ በሰላም ማስከበር እና በልማት ትብብር ረገድ ያሳለፈቻቸው ዓመታት በክብር ይወሳሉ።
እ.አ.አ በ1945 ተመድ ሲመሠረት፣ ኢትዮጵያ ቻርተሩን ከፈረሙ 51 ቀዳሚ መሥራች ሀገራት መካከል አንዷ ነበረች።
ይህም በወቅቱ በቀኝ ግዛት ሥር ለነበሩት በርካታ የአፍሪካ እና የእስያ ሀገራት ትልቅ የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀ ታሪካዊ ክስተት ነበር።
ታዲያ ይህ ግንኙነት ለሌሎች ሀገራት ከተስፋነት በዘለለ፣ ላለፉት 80 ዓመታት ጠንካራ አህጉራዊ እና ዓለም አቀፋዊ ይዘት ኖሮት ቀጥሏል።
በተባበሩት መንግሥታት የታሪክ ድርሳን ውስጥ የኢትዮጵያ ስም ጎልቶ ከሚነሳባቸው ተግባራት ቀዳሚው የሰላም ማስከበር ተልዕኮ ነው።
ከ1950ዎቹ የኮሪያ ጦርነት ጀምሮ በኮንጎ፣ በሩዋንዳ፣ በቡሩንዲ፣ በላይቤሪያ፣ በዳርፉር እንዲሁም በቅርብ ጊዜያት በአብዬ እና በደቡብ ሱዳን የሰላም ማስከበር ተልዕኮዎች ኢትዮጵያ ለሌሎች ሀገራት ሰላም ዘብ በመቆም ግንባር ቀደም ሚናዋን ተወጥታለች።
ኢትዮጵያ ለተመድ የሰላም ማስከበር ተልዕኮ በርካታ የሰላም አስከባሪ ወታደሮችን በመላክ ከግንባር ቀደምት ሀገራት ተርታ የምትሰለፍ ሆና ቀጥላለች፡፡ ይህም ለዓለም ሰላም እና መረጋጋት ያላትን ፅኑ አቋም በተግባር ያሳየችበት ነው።
አዲስ አበባ የድርጅቱ የአፍሪካ ኢኮኖሚ ኮሚሽን (ECA) እና የሌሎች በርካታ የተመድ ኤጀንሲዎች መቀመጫ መሆኗ የኢትዮጵያና የተባበሩት መንግሥታት ግንኙነት ሌላው ትልቅ መገለጫ ነው።
እ.አ.አ በ1958 የተመሰረተው ይህ ኮሚሽን አዲስ አበባን ከኒውዮርክ እና ከጄኔቫ በመቀጠል የዓለም አቀፍ ዲፕሎማሲ ማዕከል እንድትሆን አድርጓታል።
ይህ ትብብር ኢትዮጵያ በአህጉራዊ የልማት አጀንዳዎች እና በኢኮኖሚ ትሥሥር ዙሪያ ያላትን ሚና በከፍተኛ ሁኔታ አሳድጎታል።
ተመድ 80ኛ ዓመቱን ሲያከብር ኢትዮጵያ የድርጅቱ ቻርተር እንዲከበር፣ የአፍሪካ ድምፅ በፀጥታው ምክር ቤት ውሳኔ ሰጪነት ውስጥ ጉልህ ስፍራ እንዲኖረው እና በዘላቂ የልማት ግቦች ስኬት ዙሪያ ከተባበሩት መንግሥታት ጋር ያላትን አጋርነት እያጠናከረች ትገኛለች።
የኢትዮጵያና የተባበሩት መንግሥታት የ80 ዓመታት ጉዞ፣ ለቀጣዩ ትውልድም በጠንካራ መሠረት ላይ ተገንብቶ ዘላቂ ተጽዕኖ እየፈጠረ እንደሚቀጥል ይታመናል።
በሀና ምንዳሁን
#ethiopia #ebc #un80 #unitednations #peacekeeping #globaldiplomacy #uneca
****************
በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት (ተመድ) የስምንት ዐሥርተ ዓመታት ጉዞ ውስጥ፣ ኢትዮጵያ በጋራ ደኅንነት፣ በሰላም እና በልማት ፅኑ አቋም ይዛ በዓለም አቀፍ መድረክ ደማቅ አሻራዋን አኑራለች።
ይህ ከትውልድ ወደ ትውልድ የተሻገረው የባለብዙ ወገን ዲፕሎማሲ ጉዞ ተመድ የተመሠረተበትን በዓል ሲያከብር፣ የድርጅቱ ቀዳሚ መሥራች እና ንቁ ተሳታፊ የሆነችው ሀገራችን በዓለም አቀፍ ዲፕሎማሲ፣ በሰላም ማስከበር እና በልማት ትብብር ረገድ ያሳለፈቻቸው ዓመታት በክብር ይወሳሉ።
እ.አ.አ በ1945 ተመድ ሲመሠረት፣ ኢትዮጵያ ቻርተሩን ከፈረሙ 51 ቀዳሚ መሥራች ሀገራት መካከል አንዷ ነበረች።
ይህም በወቅቱ በቀኝ ግዛት ሥር ለነበሩት በርካታ የአፍሪካ እና የእስያ ሀገራት ትልቅ የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀ ታሪካዊ ክስተት ነበር።
ታዲያ ይህ ግንኙነት ለሌሎች ሀገራት ከተስፋነት በዘለለ፣ ላለፉት 80 ዓመታት ጠንካራ አህጉራዊ እና ዓለም አቀፋዊ ይዘት ኖሮት ቀጥሏል።
በተባበሩት መንግሥታት የታሪክ ድርሳን ውስጥ የኢትዮጵያ ስም ጎልቶ ከሚነሳባቸው ተግባራት ቀዳሚው የሰላም ማስከበር ተልዕኮ ነው።
ከ1950ዎቹ የኮሪያ ጦርነት ጀምሮ በኮንጎ፣ በሩዋንዳ፣ በቡሩንዲ፣ በላይቤሪያ፣ በዳርፉር እንዲሁም በቅርብ ጊዜያት በአብዬ እና በደቡብ ሱዳን የሰላም ማስከበር ተልዕኮዎች ኢትዮጵያ ለሌሎች ሀገራት ሰላም ዘብ በመቆም ግንባር ቀደም ሚናዋን ተወጥታለች።
ኢትዮጵያ ለተመድ የሰላም ማስከበር ተልዕኮ በርካታ የሰላም አስከባሪ ወታደሮችን በመላክ ከግንባር ቀደምት ሀገራት ተርታ የምትሰለፍ ሆና ቀጥላለች፡፡ ይህም ለዓለም ሰላም እና መረጋጋት ያላትን ፅኑ አቋም በተግባር ያሳየችበት ነው።
አዲስ አበባ የድርጅቱ የአፍሪካ ኢኮኖሚ ኮሚሽን (ECA) እና የሌሎች በርካታ የተመድ ኤጀንሲዎች መቀመጫ መሆኗ የኢትዮጵያና የተባበሩት መንግሥታት ግንኙነት ሌላው ትልቅ መገለጫ ነው።
እ.አ.አ በ1958 የተመሰረተው ይህ ኮሚሽን አዲስ አበባን ከኒውዮርክ እና ከጄኔቫ በመቀጠል የዓለም አቀፍ ዲፕሎማሲ ማዕከል እንድትሆን አድርጓታል።
ይህ ትብብር ኢትዮጵያ በአህጉራዊ የልማት አጀንዳዎች እና በኢኮኖሚ ትሥሥር ዙሪያ ያላትን ሚና በከፍተኛ ሁኔታ አሳድጎታል።
ተመድ 80ኛ ዓመቱን ሲያከብር ኢትዮጵያ የድርጅቱ ቻርተር እንዲከበር፣ የአፍሪካ ድምፅ በፀጥታው ምክር ቤት ውሳኔ ሰጪነት ውስጥ ጉልህ ስፍራ እንዲኖረው እና በዘላቂ የልማት ግቦች ስኬት ዙሪያ ከተባበሩት መንግሥታት ጋር ያላትን አጋርነት እያጠናከረች ትገኛለች።
የኢትዮጵያና የተባበሩት መንግሥታት የ80 ዓመታት ጉዞ፣ ለቀጣዩ ትውልድም በጠንካራ መሠረት ላይ ተገንብቶ ዘላቂ ተጽዕኖ እየፈጠረ እንደሚቀጥል ይታመናል።
በሀና ምንዳሁን
#ethiopia #ebc #un80 #unitednations #peacekeeping #globaldiplomacy #uneca