3 hours ago
ሴንቸሪ ኢንቨስትመንት ግሩፕ እና ኩባንያዎቹ ምን እየሰሩ ነው?
👉የብረት ፋብሪካው በከፍተኛ ኢንቨስትመንት ከአካባቢ ብከላ ነጻ የሆነ የምርት ሂደት መጀመሩ ተነግሯል፡፡
በሴንቸሪ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ስር የሚገኙት ስቲሊ አር ኤም አይ እና አስመን ኃ/የተ/ግ/ማ እንደ አገር በአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን የተቀመጠውን የኢንደስትሪ ቅጥር ግቢ ሁለት በመቶ ከባቢ በአረንገዴ የመሸፈን ሃላፊነት ተወጥተው ኢንደስትሪዎቹ በሚገኙበት አቅራቢያ የማህበረሰብ አቀፍ የአካባቢ ልማት ላይ በጉልህ መሳተፍ እንደቀጠሉ ተገለጠ፡፡
ባለፉት ሁለት አስርት አመታት ኢንደስትሪዎቹ በሚገኙበት የቢሾፍቱ ከተማ ቅጥር ግቢ እና አካባቢው በሚገኙ የተራቆቱ ስፍራዎቸን በአረንጓዴ የመሸፈን ስራ አጠናክረው የቀጠለ መሆኑ ታውቋል፡፡
በዚህም ዘንድሮው የክረምት ወቅት ከመንግስት ተረክበው መልሶ እንዲያገግም እየተንከባከቡት በሚገኘው ዲባዬ ተራራ በተከታታይ ለ 5ኛ አመት የተከላ መርሃ ግብር ተከናውኗል፡፡
ሀሙስ ሐምሌ 30 ቀን በተከናወነው እና የሁለቱ ኩባንያ ሰራተኞች በተሳተፉበት የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የቢሾፍቱ ከተማ የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ፅ/ቤት ኃላፊ ጣይቱ ያሚ የሁለቱ ድርጅቶች የአረንጓዴ ልማት ተግባር በአካባቢው ለሚገኙ በርካታ ኢንደስትሪዎች አርአያ እና ቀዳሚ ነው ብለዋል፡፡
እንደ አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ከኢንደስትሪ ግቢ 2 በመቶ በአረንጓዴ መሸፈን አለበት የሚለውን ህግ በተገቢው ሁለቱም ድርጅቶች መወጣታቸውን አስታውሰው፡፡
በተጨማሪነት በሴንቸሪ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ስር የሚገኙት ስቲሊ አር ኤም አይ እና አስመን ከኢንደስትሪ ስፍራዎቻቸው ባለፈ በአዋሳኝ የመንገድ አካባቢዎች እንዲሁም የተራቆቱ ቦታዎችን ወደ ጫካ የመለወጥ ስራን እንዲወጡ በከተማ አስተዳደሩ የተሰጣቸውን ቦታዎች በዛፍ የመሸፈን ስራ ለአመታት በከፍተኛ ሃላፊነት ሲሰሩ እንደቆዩ ነው የተናገሩት፡፡
ከተማ አሰስተዳደሩ በአረንጓዴ ልማት ሆነ ሌሎች ማህበራዊ ሃላፊነት ስራዎች ጥሪ ባደረገ ጊዜ ቀድመው የሚገኙ መሆናቸውን ያስታወሱት የከተማ አስተዳደሩ የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ፅ/ቤት ሃላፊ ወ/ሮ ጣይቱ ይህን መልካም ተግባር ሌሎች በተሞክሮ እንዲወስዱት ነው ያሳሰቡት፡፡
በተከላው ወቅት የግዙፉ ብረት አምራች ስቲሊ አር ኤም አይ ስራ አስኪያጅ ኢ/ር ሰለሞን ደስታ እንደገለፁት ድርጅታቸው ስቲሊ በመርህ ደረጃ የተያዘውን የማህበራዊ ሃላፊነት የመወጣት ተግባር በህብረተሰብ ድጋፍ ላይ ብቻ ያተኮረ አለመሆኑን አስታውሰው፡፡
በአካባቢ ጠበቃ የሚሰራው ስራ የኩባንያው አይነተኛ መርህ መሆኑን እንደ ተጨማሪ የማህበራዊ ሃላፊነት ስራ ተግባር ለአብነት አንስተዋል፡፡
በዚህም ስቲሊ አር ኤም አይ ማምረት ከጀመረበት ያለፉት ሁለት አስርት አመታት ወደ ስራ ካስገባቸው እንደ ዘመናዊ ትምህርት ቤት እንዲሁም የውሃ አቅርቦት አይነት ጉልህ ማህበራዊ ሃላፊነት ባልተናነሰ በአረንጓዴ ልማት ከፍተኛ ስራ ተሰርቷል ብለዋል፡፡
በግቢያችን በመንግስት ከተቀመጠው የሁለት በመቶ አረንጓዴ ሽፋን አልፈናል ያሉት ኢ/ር ሰለሞን ለምግብነት የሚያገለግሉ ዛፎችን የመትከል ግቡም ውጤታማ እየሆነልን ነው ሲሉ ነው ያከሉት።
ዋና ስራ አስኪያጁ በተጨማሪነት በአካበቢው በሚገኙ ተራራማ ቦታዎች ችግኝ በመትከል እና በቋሚነት ባለሞያ ቀጥሮ በመንከባከብ ከፍተኛ ውጤት ማስገኘት መቻሉንም እንደ ከፍተኛ ተጠቃሽ ውጤት አንስተዋል፡፡
በተጨማሪም ኩባያው ከፍተኛ ኢንቨስትመንት በማድረግ ዘመናዊ የምርት ሂደትን ያስተዋወቀ መሆኑን ጠቅሰው። ይህም የአካባቢ ጥበቃ አካል ነው ሲሉ በአገር ደረጃ በዘመናዊነት ቀዳሚ የሆነው የብረት ፋብሪካ የስራ ሂደት ጠቅሰዋል፡፡
በተመሳሳይ ከፍተኛ ተኪ የብረት ምርት እና የግንባታ ግብአቶችን በማምረት ላለፉት ሩብ ክፍለ ዘመናት መቆየት የቻለው የአስመን ስራ አስኪያጅ አቶ ኑሩ እሸቱ የአረንጓዴ አሻራ ስራ የኩባንያቸው ባህል መሆኑን ጠቅሰው በቀጣይ ይህ ተግባር ተጠናክሮ የሚቀጠል መሆኑን ነው የገለፁት፡፡
እንደ አስመን ስራ አስኪያጅ ገለፃ የኩባንያውን ሰራተኛና የአካበባቢውን ነዋሪ በማሳተፍ ሲከናወን የቆየው የአካባቢ ጥበቃ ስራ በተለይ አሁን በፋብሪካዎቹ እና የችግኝ ተከላ በሚከናወንበት አቅራቢያ በሚገኘው በአቡሴራ እየተገነባ የሚገኘው የቢሾፍቱ አየር መንገድ ምቹ እና አረንጓዴ ከባቢ በመፍጠር የራሱ ሚና አለው ሲሉ ነው የገለጹት፡፡
የሴንቸሪ ኢንቨስትመንት ግሩፕ የቦርድ ተወካይ አቶ ግርማ አዲስ በበኩላቸው ስቲሊ አር ኤም አይ እና አስመን አረጋውያን የማገዝ፣ ተንከባካቢ የሌላቸው ህጻናትን ከጎናቸው በመሆን አሌንታነት በማረጋገጥ፣ የምገባ ማዕከላትን በማቋቋም፣ በተለያየ ምክንያት እና እንደ የተፈጥሮ እና ሰው ሰራሽ አደጋ አይነት አጣዳፊ ሁኔታ ሲያጋጥም ድጋፍ ለሚሹ ወገኖች ድጋፍ በማድረግ የወገን ደራሽ የመሆን ሚናቸውን ከምስረታቸው ጀምሮ እንደተገበሩ ገልፀዋል፡፡
ይህንኑ ተግባር ወደ ፊትም በተቀናጀ መልኩ እንደ ግሩፕ ለማከናወን ፋውንዴሽን መቋቋሙን ነው አክለው የገለጹት፡፡
👉የብረት ፋብሪካው በከፍተኛ ኢንቨስትመንት ከአካባቢ ብከላ ነጻ የሆነ የምርት ሂደት መጀመሩ ተነግሯል፡፡
በሴንቸሪ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ስር የሚገኙት ስቲሊ አር ኤም አይ እና አስመን ኃ/የተ/ግ/ማ እንደ አገር በአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን የተቀመጠውን የኢንደስትሪ ቅጥር ግቢ ሁለት በመቶ ከባቢ በአረንገዴ የመሸፈን ሃላፊነት ተወጥተው ኢንደስትሪዎቹ በሚገኙበት አቅራቢያ የማህበረሰብ አቀፍ የአካባቢ ልማት ላይ በጉልህ መሳተፍ እንደቀጠሉ ተገለጠ፡፡
ባለፉት ሁለት አስርት አመታት ኢንደስትሪዎቹ በሚገኙበት የቢሾፍቱ ከተማ ቅጥር ግቢ እና አካባቢው በሚገኙ የተራቆቱ ስፍራዎቸን በአረንጓዴ የመሸፈን ስራ አጠናክረው የቀጠለ መሆኑ ታውቋል፡፡
በዚህም ዘንድሮው የክረምት ወቅት ከመንግስት ተረክበው መልሶ እንዲያገግም እየተንከባከቡት በሚገኘው ዲባዬ ተራራ በተከታታይ ለ 5ኛ አመት የተከላ መርሃ ግብር ተከናውኗል፡፡
ሀሙስ ሐምሌ 30 ቀን በተከናወነው እና የሁለቱ ኩባንያ ሰራተኞች በተሳተፉበት የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የቢሾፍቱ ከተማ የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ፅ/ቤት ኃላፊ ጣይቱ ያሚ የሁለቱ ድርጅቶች የአረንጓዴ ልማት ተግባር በአካባቢው ለሚገኙ በርካታ ኢንደስትሪዎች አርአያ እና ቀዳሚ ነው ብለዋል፡፡
እንደ አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ከኢንደስትሪ ግቢ 2 በመቶ በአረንጓዴ መሸፈን አለበት የሚለውን ህግ በተገቢው ሁለቱም ድርጅቶች መወጣታቸውን አስታውሰው፡፡
በተጨማሪነት በሴንቸሪ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ስር የሚገኙት ስቲሊ አር ኤም አይ እና አስመን ከኢንደስትሪ ስፍራዎቻቸው ባለፈ በአዋሳኝ የመንገድ አካባቢዎች እንዲሁም የተራቆቱ ቦታዎችን ወደ ጫካ የመለወጥ ስራን እንዲወጡ በከተማ አስተዳደሩ የተሰጣቸውን ቦታዎች በዛፍ የመሸፈን ስራ ለአመታት በከፍተኛ ሃላፊነት ሲሰሩ እንደቆዩ ነው የተናገሩት፡፡
ከተማ አሰስተዳደሩ በአረንጓዴ ልማት ሆነ ሌሎች ማህበራዊ ሃላፊነት ስራዎች ጥሪ ባደረገ ጊዜ ቀድመው የሚገኙ መሆናቸውን ያስታወሱት የከተማ አስተዳደሩ የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ፅ/ቤት ሃላፊ ወ/ሮ ጣይቱ ይህን መልካም ተግባር ሌሎች በተሞክሮ እንዲወስዱት ነው ያሳሰቡት፡፡
በተከላው ወቅት የግዙፉ ብረት አምራች ስቲሊ አር ኤም አይ ስራ አስኪያጅ ኢ/ር ሰለሞን ደስታ እንደገለፁት ድርጅታቸው ስቲሊ በመርህ ደረጃ የተያዘውን የማህበራዊ ሃላፊነት የመወጣት ተግባር በህብረተሰብ ድጋፍ ላይ ብቻ ያተኮረ አለመሆኑን አስታውሰው፡፡
በአካባቢ ጠበቃ የሚሰራው ስራ የኩባንያው አይነተኛ መርህ መሆኑን እንደ ተጨማሪ የማህበራዊ ሃላፊነት ስራ ተግባር ለአብነት አንስተዋል፡፡
በዚህም ስቲሊ አር ኤም አይ ማምረት ከጀመረበት ያለፉት ሁለት አስርት አመታት ወደ ስራ ካስገባቸው እንደ ዘመናዊ ትምህርት ቤት እንዲሁም የውሃ አቅርቦት አይነት ጉልህ ማህበራዊ ሃላፊነት ባልተናነሰ በአረንጓዴ ልማት ከፍተኛ ስራ ተሰርቷል ብለዋል፡፡
በግቢያችን በመንግስት ከተቀመጠው የሁለት በመቶ አረንጓዴ ሽፋን አልፈናል ያሉት ኢ/ር ሰለሞን ለምግብነት የሚያገለግሉ ዛፎችን የመትከል ግቡም ውጤታማ እየሆነልን ነው ሲሉ ነው ያከሉት።
ዋና ስራ አስኪያጁ በተጨማሪነት በአካበቢው በሚገኙ ተራራማ ቦታዎች ችግኝ በመትከል እና በቋሚነት ባለሞያ ቀጥሮ በመንከባከብ ከፍተኛ ውጤት ማስገኘት መቻሉንም እንደ ከፍተኛ ተጠቃሽ ውጤት አንስተዋል፡፡
በተጨማሪም ኩባያው ከፍተኛ ኢንቨስትመንት በማድረግ ዘመናዊ የምርት ሂደትን ያስተዋወቀ መሆኑን ጠቅሰው። ይህም የአካባቢ ጥበቃ አካል ነው ሲሉ በአገር ደረጃ በዘመናዊነት ቀዳሚ የሆነው የብረት ፋብሪካ የስራ ሂደት ጠቅሰዋል፡፡
በተመሳሳይ ከፍተኛ ተኪ የብረት ምርት እና የግንባታ ግብአቶችን በማምረት ላለፉት ሩብ ክፍለ ዘመናት መቆየት የቻለው የአስመን ስራ አስኪያጅ አቶ ኑሩ እሸቱ የአረንጓዴ አሻራ ስራ የኩባንያቸው ባህል መሆኑን ጠቅሰው በቀጣይ ይህ ተግባር ተጠናክሮ የሚቀጠል መሆኑን ነው የገለፁት፡፡
እንደ አስመን ስራ አስኪያጅ ገለፃ የኩባንያውን ሰራተኛና የአካበባቢውን ነዋሪ በማሳተፍ ሲከናወን የቆየው የአካባቢ ጥበቃ ስራ በተለይ አሁን በፋብሪካዎቹ እና የችግኝ ተከላ በሚከናወንበት አቅራቢያ በሚገኘው በአቡሴራ እየተገነባ የሚገኘው የቢሾፍቱ አየር መንገድ ምቹ እና አረንጓዴ ከባቢ በመፍጠር የራሱ ሚና አለው ሲሉ ነው የገለጹት፡፡
የሴንቸሪ ኢንቨስትመንት ግሩፕ የቦርድ ተወካይ አቶ ግርማ አዲስ በበኩላቸው ስቲሊ አር ኤም አይ እና አስመን አረጋውያን የማገዝ፣ ተንከባካቢ የሌላቸው ህጻናትን ከጎናቸው በመሆን አሌንታነት በማረጋገጥ፣ የምገባ ማዕከላትን በማቋቋም፣ በተለያየ ምክንያት እና እንደ የተፈጥሮ እና ሰው ሰራሽ አደጋ አይነት አጣዳፊ ሁኔታ ሲያጋጥም ድጋፍ ለሚሹ ወገኖች ድጋፍ በማድረግ የወገን ደራሽ የመሆን ሚናቸውን ከምስረታቸው ጀምሮ እንደተገበሩ ገልፀዋል፡፡
ይህንኑ ተግባር ወደ ፊትም በተቀናጀ መልኩ እንደ ግሩፕ ለማከናወን ፋውንዴሽን መቋቋሙን ነው አክለው የገለጹት፡፡
5 hours ago
የኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር አዘዘው ጫኔ በተደራጀ የኢኮኖሚ ወንጀል ተጠርጥረው በቁጥጥር ስር ከዋሉት 91 ግለሰቦች መሀል ይገኙበታል ተባለ
በጉዳዩ ላይ ከተካሄደው ምርመራ ከተገኙ ግኝቶች መካከል፡-
👉በገቢዎች እና ጉምሩክ አስተዳደር ውስጥ የተደራጀ ህገ-ወጥ መረብ መኖሩ ተጠቁሟል።
👉የታክስ ምዘናዎችን ማሻሻጥ፣ ሀሰተኛ ደረሰኞችን ማስተናገድ እና የኤሌክትሮኒክስ መረጃዎችን መሰረዝ እንደ ዘዴ ጥቅም ላይ ውለዋል ተብሏል።
👉ድርጊቶቹ የመንግስት ገቢ እንዲቀንስ ማድረጋቸው ተመልክቷል።
በአሁኑ ወቅት ጉዳዩ በህግ አስከባሪ አካላት ተይዞ ምርመራው በዝርዝር እየተካሄደ ይገኛል።
Seledadotio
Seledadotio
በጉዳዩ ላይ ከተካሄደው ምርመራ ከተገኙ ግኝቶች መካከል፡-
👉በገቢዎች እና ጉምሩክ አስተዳደር ውስጥ የተደራጀ ህገ-ወጥ መረብ መኖሩ ተጠቁሟል።
👉የታክስ ምዘናዎችን ማሻሻጥ፣ ሀሰተኛ ደረሰኞችን ማስተናገድ እና የኤሌክትሮኒክስ መረጃዎችን መሰረዝ እንደ ዘዴ ጥቅም ላይ ውለዋል ተብሏል።
👉ድርጊቶቹ የመንግስት ገቢ እንዲቀንስ ማድረጋቸው ተመልክቷል።
በአሁኑ ወቅት ጉዳዩ በህግ አስከባሪ አካላት ተይዞ ምርመራው በዝርዝር እየተካሄደ ይገኛል።
Seledadotio
Seledadotio
8 hours ago
ከ4መቶ በላይ ፌስታል የሚያመርቱ ተቋማት ላይ ክትትልና ቁጥጥር ማድረጉን የአዲስ አበባ አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ተናገረ
ባለስልጣኑ የፕላስቲክ ምርቶች ለገበያ እንዳይቀርቡና ምርቱም እንዲቆም የሚያደርገዉ ህግ ወደ ስራ መግባቱን ተከትሎ ቁጥጥር እያደረጉ እገኛለሁ ብሏል።
በዚህም መሠረት በተጠናቀቀው በጀት አመት ከረጢት ስራ ላይ እንዳይውል ለማድረግ በተሰራው ስራ 4መቶ 88 ፌስታል የሚያመርቱ ተቋማት ላይ ክትትልና ቁጥጥር ተደርጓል ተብሏል።
አሁንም በርካታ የምርት ክምችቶች በቁጥጥር ስር እየዋሉ እንደሚገኝ የገልፁት የባለስልጣኑ ዋና አማካሪ አቶ አዱኛ ወንድሙ ባለስልጣኑ በደረሰበት ልክ ክትትል እያደረገ ቢሆንም ህብረተሰቡ ስለፌስታል ያለውን ግንዛቤ መቀየር ካልተቀየሩ ምርቱን በቀላሉ ማስቆም እንዳልተቻለ ተናግረዋል።
አምራች ተቋማቱ ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ እና ወደ ሌሎች ተኪ ምርቶች እንዲሰማሩ በማድረግ ያላሻሻሉት ላይ እስከማሸግ የደረሰ እርምጃ መውሰድ እንደተቻለም አያይዙዉ ገልፀዋል።
በበጀት አመቱ ከብክለት ጋር በተያያዘ ከ17ሺ 1መቶ በላይ ተቋማት ላይ ባደረገው ክትትልና ቁጥጥር መደረጉ ተነግሯል።
ህግ ተላልፈው የተገኙ 3ሺ 3መቶ 18 ተቋማት ላይ አስተዳደራዊ እርምጃ ተወስዷልም ተብሏል።
ቁምነገር አየለ
ባለስልጣኑ የፕላስቲክ ምርቶች ለገበያ እንዳይቀርቡና ምርቱም እንዲቆም የሚያደርገዉ ህግ ወደ ስራ መግባቱን ተከትሎ ቁጥጥር እያደረጉ እገኛለሁ ብሏል።
በዚህም መሠረት በተጠናቀቀው በጀት አመት ከረጢት ስራ ላይ እንዳይውል ለማድረግ በተሰራው ስራ 4መቶ 88 ፌስታል የሚያመርቱ ተቋማት ላይ ክትትልና ቁጥጥር ተደርጓል ተብሏል።
አሁንም በርካታ የምርት ክምችቶች በቁጥጥር ስር እየዋሉ እንደሚገኝ የገልፁት የባለስልጣኑ ዋና አማካሪ አቶ አዱኛ ወንድሙ ባለስልጣኑ በደረሰበት ልክ ክትትል እያደረገ ቢሆንም ህብረተሰቡ ስለፌስታል ያለውን ግንዛቤ መቀየር ካልተቀየሩ ምርቱን በቀላሉ ማስቆም እንዳልተቻለ ተናግረዋል።
አምራች ተቋማቱ ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ እና ወደ ሌሎች ተኪ ምርቶች እንዲሰማሩ በማድረግ ያላሻሻሉት ላይ እስከማሸግ የደረሰ እርምጃ መውሰድ እንደተቻለም አያይዙዉ ገልፀዋል።
በበጀት አመቱ ከብክለት ጋር በተያያዘ ከ17ሺ 1መቶ በላይ ተቋማት ላይ ባደረገው ክትትልና ቁጥጥር መደረጉ ተነግሯል።
ህግ ተላልፈው የተገኙ 3ሺ 3መቶ 18 ተቋማት ላይ አስተዳደራዊ እርምጃ ተወስዷልም ተብሏል።
ቁምነገር አየለ
15 hours ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ፣ የሀገሪቱን የትውልድ ዜግነት መብት ለመገደብ ያለመ አዲስ ነገር ግን ጠበብ ያለ ማዕቀፍ ያላቸውን ሁለት አስፈጻሚ ትዕዛዞች ሐሙስ ዕለት ፈርመዋል። ይህ አዲስ እርምጃ፣ ፕሬዝዳንቱ ቀደም ሲል ያወጡት ተመሳሳይ ትዕዛዝ በጠቅላይ ፍርድ ቤት ውድቅ መደረጉን ተከትሎ፣ የአሜሪካን ህገ-መንግስት ድንጋጌ ዳግም ለመሞገት የተደረገ ሙከራ ነው።
በትራምፕ የሪፐብሊካን አስተዳደር የጸረ-ስደተኞች ፖሊሲ ውስጥ የትውልድ ዜግነትን መገደብ ቀዳሚው አጀንዳ ሆኖ ቆይቷል። በተለይም ነፍሰጡር የውጭ ዜጎች ልጆቻቸውን በአሜሪካ ምድር በመውለድ ዜግነት ለማግኘት የሚያደርጉትን ጉዞ ወይም ዋይት ሀውስ "የወሊድ ቱሪዝም" በማለት የሚጠራውን አሰራር ዋነኛ ኢላማው አድርጓል።
ባለፈው ሰኔ 30 ጠቅላይ ፍርድ ቤቱ የትራምፕን የመጀመሪያ ትዕዛዝ "ከህገ-መንግስቱ ጋር የሚጻረር ነው" በማለት ውድቅ ማድረጉን ተከትሎ፣ ፕሬዝዳንቱ ኮንግረሱ ህግ እንዲያወጣ ጥሪ አቅርበው ነበር። ሆኖም ሐሙስ ዕለት ፖሊሲን የሚያወጡ ነገር ግን የህግ አስገዳጅነት የሌላቸውን አስፈጻሚ ትዕዛዞችን መፈረምን መርጠዋል። የትራምፕ አስተዳደር እንደሚለው፣ እነዚህ አዳዲስ መመሪያዎች ጠቅላይ ፍርድ ቤቱ ካስቀመጣቸው ገደቦች ውጪ የሆኑ ናቸው። ይህም የወሊድ ቱሪዝምን ጨምሮ የትውልድ ዜግነት መብት የማይገባቸውን ሰዎች ምድብ ለማስፋት ያስችለዋል ብሏል። በትራምፕ ትዕዛዝ መሰረት፣ እነዚህ ምድቦች "ጠቅላይ ፍርድ ቤቱ ካወጀው የትውልድ ዜግነት ደንብ ስር አይወድቁም።"
በዋይት ሀውስ የፕሬዝዳንቱ ረዳት የሆኑት ስቴፈን ሚለር በትዕዛዙ የፊርማ ስነ-ስርዓት ላይ፣ "ይህ ትዕዛዝ ከተፈረመበት ጊዜ ጀምሮ የወሊድ ቱሪዝም ልምምድ ሙሉ በሙሉ ታግዷል። ይህ ማለት ማንም ሰው ለዚህ አታላይ ዓላማ ቪዛ ማግኘት አይፈቀድለትም" ሲሉ ተናግረዋል።
አዳዲሶቹ ትዕዛዞች ከወሊድ ቱሪዝም ባሻገር፣ በአሜሪካ ለሚገኙ የውጭ መንግስታት ሰራተኞች እና እንደ 'ጠላት' (Alien Enemies) ለተፈረጁ የውጭ ዜጎች የሚወለዱ ልጆችን የዜግነት መብት ይገድባሉ። ከዚህም በተጨማሪ ኮንግረሱ አዲስ ህግ ካጸደቀ፣ በአሜሪካ ግዛቶች (Territories) ውስጥ የሚወለዱ ሰዎች አውቶማቲክ ዜግነት እንዳያገኙ ሊያደርግ እንደሚችል ተጠቁሟል።
ፕሬዝዳንት ትራምፕ በጠቅላይ ፍርድ ቤቱ የተሰጠውን የ6 ለ 3 የድምጽ ውሳኔ አጥብቀው ተችተዋል። "በትውልድ ዜግነት ላይ ከጠቅላይ ፍርድ ቤቱ እጅግ አሳዛኝ ውሳኔ አጋጥሞናል... በጣም ተቀራራቢ ድምጽ ቢሆንም፣ እጅግ አሳዛኝ ውሳኔ ነው" ብለዋል። አክለውም፣ "ሰዎች ዜግነትን ማግኛ መንገድ አድርገው ንግድ እየገነቡበት ነው። አሰራሩ እንደዚህ መሆን አልነበረበትም፤ ይህ አሳፋሪ ነው። ዜግነትን በገንዘብ እየገዙ ነው፣ እኛ ደግሞ ይህ እንዲሆን አንፈቅድም" ሲሉ ቅሬታቸውን ገልጸዋል።
የአሜሪካ ህገ-መንግስት 14ኛው ማሻሻያ ከውጭ ዲፕሎማቶች ወይም ወራሪ የጠላት ኃይል አባላት ልጆች ውጪ፣ በአሜሪካ ምድር ለሚወለዱ ህጻናት በሙሉ የዜግነት መብትን እንደሚያረጋግጥ በህግ ሲተረጎም ቆይቷል። ትራምፕ ግን ይህ ህግ የወጣው ከእርስ በርስ ጦርነቱ በኋላ ለባሮች ልጆች ዜግነት ለመስጠት መሆኑን በመጥቀስ፣ የአሁኑ አሰራር የህጉን መንፈስ የሳተ ነው ብለዋል።
በሌላ በኩል የጠቅላይ ፍርድ ቤቱ ዋና ዳኛ ጆን ሮበርትስ በውሳኔያቸው ላይ፣ የ14ኛው ማሻሻያ አርቃቂዎች ይህንን ቃል ኪዳን በሀገሪቱ ውስጥ ለተወለደ እያንዳንዱ ነጻ ሰው እንዳሰፉት አስታውሰው፣ "ዜግነት በዚያን ጊዜም ሆነ አሁን መብቶችን የማግኘት እና በፖለቲካዊ ማህበረሰባችን ውስጥ በነጻነት የመሳተፍ መብት ነው። ይህንን ቃል ኪዳን ዛሬም እንጠብቃለን" በማለት የህገ-መንግስቱን ሰፊ ትርጉም አጽንኦት ሰጥተውበታል።
በ2020 የትራምፕ የመጀመሪያ የስልጣን ዘመን አዲስ የተወለደ ልጅ የአሜሪካ ዜግነት እንዲያገኝ በሚል ዓላማ የቱሪስት እና የንግድ ቪዛዎችን መጠቀምን የሚከለክል የፌዴራል ደንብ ወጥቶ የነበረ ቢሆንም፣ የወሊድ ቱሪዝምን ሙሉ በሙሉ የሚከለክል ግልጽ ህግ በአሜሪካ የለም። ይህን መሰል ማጭበርበር ላይ የሚሳተፉ ሰዎች በህግ ሊጠየቁ ቢችሉም፣ የትራምፕ አዳዲስ አስፈጻሚ ትዕዛዞች በፍርድ ቤቶች በኩል ጠንካራ የህግ ተግዳሮት እንደሚገጥማቸው በሰፊው ይጠበቃል።
በትራምፕ የሪፐብሊካን አስተዳደር የጸረ-ስደተኞች ፖሊሲ ውስጥ የትውልድ ዜግነትን መገደብ ቀዳሚው አጀንዳ ሆኖ ቆይቷል። በተለይም ነፍሰጡር የውጭ ዜጎች ልጆቻቸውን በአሜሪካ ምድር በመውለድ ዜግነት ለማግኘት የሚያደርጉትን ጉዞ ወይም ዋይት ሀውስ "የወሊድ ቱሪዝም" በማለት የሚጠራውን አሰራር ዋነኛ ኢላማው አድርጓል።
ባለፈው ሰኔ 30 ጠቅላይ ፍርድ ቤቱ የትራምፕን የመጀመሪያ ትዕዛዝ "ከህገ-መንግስቱ ጋር የሚጻረር ነው" በማለት ውድቅ ማድረጉን ተከትሎ፣ ፕሬዝዳንቱ ኮንግረሱ ህግ እንዲያወጣ ጥሪ አቅርበው ነበር። ሆኖም ሐሙስ ዕለት ፖሊሲን የሚያወጡ ነገር ግን የህግ አስገዳጅነት የሌላቸውን አስፈጻሚ ትዕዛዞችን መፈረምን መርጠዋል። የትራምፕ አስተዳደር እንደሚለው፣ እነዚህ አዳዲስ መመሪያዎች ጠቅላይ ፍርድ ቤቱ ካስቀመጣቸው ገደቦች ውጪ የሆኑ ናቸው። ይህም የወሊድ ቱሪዝምን ጨምሮ የትውልድ ዜግነት መብት የማይገባቸውን ሰዎች ምድብ ለማስፋት ያስችለዋል ብሏል። በትራምፕ ትዕዛዝ መሰረት፣ እነዚህ ምድቦች "ጠቅላይ ፍርድ ቤቱ ካወጀው የትውልድ ዜግነት ደንብ ስር አይወድቁም።"
በዋይት ሀውስ የፕሬዝዳንቱ ረዳት የሆኑት ስቴፈን ሚለር በትዕዛዙ የፊርማ ስነ-ስርዓት ላይ፣ "ይህ ትዕዛዝ ከተፈረመበት ጊዜ ጀምሮ የወሊድ ቱሪዝም ልምምድ ሙሉ በሙሉ ታግዷል። ይህ ማለት ማንም ሰው ለዚህ አታላይ ዓላማ ቪዛ ማግኘት አይፈቀድለትም" ሲሉ ተናግረዋል።
አዳዲሶቹ ትዕዛዞች ከወሊድ ቱሪዝም ባሻገር፣ በአሜሪካ ለሚገኙ የውጭ መንግስታት ሰራተኞች እና እንደ 'ጠላት' (Alien Enemies) ለተፈረጁ የውጭ ዜጎች የሚወለዱ ልጆችን የዜግነት መብት ይገድባሉ። ከዚህም በተጨማሪ ኮንግረሱ አዲስ ህግ ካጸደቀ፣ በአሜሪካ ግዛቶች (Territories) ውስጥ የሚወለዱ ሰዎች አውቶማቲክ ዜግነት እንዳያገኙ ሊያደርግ እንደሚችል ተጠቁሟል።
ፕሬዝዳንት ትራምፕ በጠቅላይ ፍርድ ቤቱ የተሰጠውን የ6 ለ 3 የድምጽ ውሳኔ አጥብቀው ተችተዋል። "በትውልድ ዜግነት ላይ ከጠቅላይ ፍርድ ቤቱ እጅግ አሳዛኝ ውሳኔ አጋጥሞናል... በጣም ተቀራራቢ ድምጽ ቢሆንም፣ እጅግ አሳዛኝ ውሳኔ ነው" ብለዋል። አክለውም፣ "ሰዎች ዜግነትን ማግኛ መንገድ አድርገው ንግድ እየገነቡበት ነው። አሰራሩ እንደዚህ መሆን አልነበረበትም፤ ይህ አሳፋሪ ነው። ዜግነትን በገንዘብ እየገዙ ነው፣ እኛ ደግሞ ይህ እንዲሆን አንፈቅድም" ሲሉ ቅሬታቸውን ገልጸዋል።
የአሜሪካ ህገ-መንግስት 14ኛው ማሻሻያ ከውጭ ዲፕሎማቶች ወይም ወራሪ የጠላት ኃይል አባላት ልጆች ውጪ፣ በአሜሪካ ምድር ለሚወለዱ ህጻናት በሙሉ የዜግነት መብትን እንደሚያረጋግጥ በህግ ሲተረጎም ቆይቷል። ትራምፕ ግን ይህ ህግ የወጣው ከእርስ በርስ ጦርነቱ በኋላ ለባሮች ልጆች ዜግነት ለመስጠት መሆኑን በመጥቀስ፣ የአሁኑ አሰራር የህጉን መንፈስ የሳተ ነው ብለዋል።
በሌላ በኩል የጠቅላይ ፍርድ ቤቱ ዋና ዳኛ ጆን ሮበርትስ በውሳኔያቸው ላይ፣ የ14ኛው ማሻሻያ አርቃቂዎች ይህንን ቃል ኪዳን በሀገሪቱ ውስጥ ለተወለደ እያንዳንዱ ነጻ ሰው እንዳሰፉት አስታውሰው፣ "ዜግነት በዚያን ጊዜም ሆነ አሁን መብቶችን የማግኘት እና በፖለቲካዊ ማህበረሰባችን ውስጥ በነጻነት የመሳተፍ መብት ነው። ይህንን ቃል ኪዳን ዛሬም እንጠብቃለን" በማለት የህገ-መንግስቱን ሰፊ ትርጉም አጽንኦት ሰጥተውበታል።
በ2020 የትራምፕ የመጀመሪያ የስልጣን ዘመን አዲስ የተወለደ ልጅ የአሜሪካ ዜግነት እንዲያገኝ በሚል ዓላማ የቱሪስት እና የንግድ ቪዛዎችን መጠቀምን የሚከለክል የፌዴራል ደንብ ወጥቶ የነበረ ቢሆንም፣ የወሊድ ቱሪዝምን ሙሉ በሙሉ የሚከለክል ግልጽ ህግ በአሜሪካ የለም። ይህን መሰል ማጭበርበር ላይ የሚሳተፉ ሰዎች በህግ ሊጠየቁ ቢችሉም፣ የትራምፕ አዳዲስ አስፈጻሚ ትዕዛዞች በፍርድ ቤቶች በኩል ጠንካራ የህግ ተግዳሮት እንደሚገጥማቸው በሰፊው ይጠበቃል።
17 hours ago
ኢትዮጵያ በአፍሪካ በዲጂታል ተጋላጭነት 5ኛ ደረጃ ላይ መሆኗን የኢንተርፖል ሪፖርት አመለከተ
#ethiopia | ኢትዮጵያ የዲጂታል ለውጥ ጉዞዋን በፍጥነት እያፋጠነች ባለችበት ወቅት፣ እየተባባሱ የሚመጡ የሳይበር ጥቃቶችን እና የዲጂታል ደህንነት ተግዳሮቶችን እየተጋፈጠች መሆኗን አዲስ የኢንተርፖል የአፍሪካ የሳይበር ስጋት ግምገማ ሪፖርት አመልክቷል።
ሪፖርቱ በ36 የአፍሪካ አባል ሀገራት እና እንደ Shadowserver Foundation ባሉ ተቋማት የተሰበሰበ መረጃን መሰረት አድርጎ የተዘጋጀ ሲሆን፣ ፈጣን የቴክኖሎጂ እድገት ከሳይበር ደህንነት አቅምና ከተቋማዊ ዝግጁነት በፍጥነት እየቀደመ መሆኑን ገልጿል።
በዚህም መሰረት ኢትዮጵያ በአፍሪካ ከተመዘገቡ የዲጂታል ተጋላጭነቶች 3.3 በመቶውን በመያዝ በአህጉሪቱ 5ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጣለች።
በመላው አፍሪካ በሳይበር ወንጀሎች የደረሰው ቀጥተኛ የኢኮኖሚ ኪሳራ 5 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር ሊጠጋ ሲችል፣ ለሳይበር ደህንነት የተደረገው ወጪ 15.3 ቢሊዮን ዶላር ደርሷል።
በተጨማሪም በሳይበር ወንጀሎች የተመዘገበው የገንዘብ ኪሳራ ከ192 ሚሊዮን ዶላር ወደ 484 ሚሊዮን ዶላር ሲጨምር፣ የተጎጂዎች ቁጥርም ከ35 ሺህ ወደ 87 ሺህ ከፍ ብሏል።
ሪፖርቱ እንደሚያሳየው በምስራቅ አፍሪካ የሳይበር ስጋት መጠን መካከለኛ እስከ ከፍተኛ ደረጃ ላይ ይገኛል። ይህም በተለይ ከሞባይል ገንዘብ ማጭበርበር፣ በቴሌኮሙኒኬሽን ዘርፍ ጥቃቶች እና ወሳኝ መሠረተ ልማቶችን የሚያነጣጥሩ የራንሰምዌር ጥቃቶች ጋር የተያያዘ ነው።
ኢንተርፖል እንደገለጸው፣ በብዛት ለጥቃት የሚጋለጡት ያልተዘመኑ የሶፍትዌር ስርዓቶች፣ ለህዝብ የተጋለጡ የVPN አገልግሎቶች እና በትክክል ያልተዋቀሩ የሰነድ አስተዳደር መድረኮች ናቸው። እንዲሁም ኢትዮጵያ 1.36 በመቶ የአፍሪካ የቦትኔት ኖዶችን እንደምታስተናግድ ተገልጿል።
በተጨማሪም በሰው ሠራሽ የማሰብ ችሎታ (AI) የሚደገፍ ዲጂታል የጾታ ማስፈራሪያ (Sextortion) እያደገ የመጣ ስጋት ሲሆን፣ ኢትዮጵያ በዚህ ዘርፍ 8 በመቶ የአህጉራዊ መለኪያ ድርሻ እንዳላት ተጠቅሷል።
ሪፖርቱ በአፍሪካ ያሉ የህግ አስከባሪ ተቋማትም ከባድ የአቅም ችግሮች እንደሚያጋጥሟቸው ያመለክታል። 94 በመቶ የሚሆኑት ተቋማት በቂ የዲጂታል ፎረንሲክስ መሳሪያዎች እንደሌላቸው ሲገልጹ፣ 78 በመቶ የበጀትና የባለሙያ እጥረት እንዳለባቸው፣ 89 በመቶዎቹ ደግሞ በሀገራት መካከል የተሻለ ትብብር አለመኖሩ ዋና ተግዳሮት መሆኑን ጠቁመዋል።
በመጨረሻም ኢንተርፖልና የሳይበር ደህንነት ባለሙያዎች መንግስታት ድንበር ተሻጋሪ ትብብርን ማጠናከር፣ የሳይበር ንፅህና መርሆችን ማሻሻል፣ የመንግስትና የግል ዘርፍ አጋርነትን ማሳደግ እንዲሁም ዘመናዊ የህግ ማዕቀፎችን ማዘጋጀት ወሳኝ መሆኑን አሳስበዋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#ethiopia | ኢትዮጵያ የዲጂታል ለውጥ ጉዞዋን በፍጥነት እያፋጠነች ባለችበት ወቅት፣ እየተባባሱ የሚመጡ የሳይበር ጥቃቶችን እና የዲጂታል ደህንነት ተግዳሮቶችን እየተጋፈጠች መሆኗን አዲስ የኢንተርፖል የአፍሪካ የሳይበር ስጋት ግምገማ ሪፖርት አመልክቷል።
ሪፖርቱ በ36 የአፍሪካ አባል ሀገራት እና እንደ Shadowserver Foundation ባሉ ተቋማት የተሰበሰበ መረጃን መሰረት አድርጎ የተዘጋጀ ሲሆን፣ ፈጣን የቴክኖሎጂ እድገት ከሳይበር ደህንነት አቅምና ከተቋማዊ ዝግጁነት በፍጥነት እየቀደመ መሆኑን ገልጿል።
በዚህም መሰረት ኢትዮጵያ በአፍሪካ ከተመዘገቡ የዲጂታል ተጋላጭነቶች 3.3 በመቶውን በመያዝ በአህጉሪቱ 5ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጣለች።
በመላው አፍሪካ በሳይበር ወንጀሎች የደረሰው ቀጥተኛ የኢኮኖሚ ኪሳራ 5 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር ሊጠጋ ሲችል፣ ለሳይበር ደህንነት የተደረገው ወጪ 15.3 ቢሊዮን ዶላር ደርሷል።
በተጨማሪም በሳይበር ወንጀሎች የተመዘገበው የገንዘብ ኪሳራ ከ192 ሚሊዮን ዶላር ወደ 484 ሚሊዮን ዶላር ሲጨምር፣ የተጎጂዎች ቁጥርም ከ35 ሺህ ወደ 87 ሺህ ከፍ ብሏል።
ሪፖርቱ እንደሚያሳየው በምስራቅ አፍሪካ የሳይበር ስጋት መጠን መካከለኛ እስከ ከፍተኛ ደረጃ ላይ ይገኛል። ይህም በተለይ ከሞባይል ገንዘብ ማጭበርበር፣ በቴሌኮሙኒኬሽን ዘርፍ ጥቃቶች እና ወሳኝ መሠረተ ልማቶችን የሚያነጣጥሩ የራንሰምዌር ጥቃቶች ጋር የተያያዘ ነው።
ኢንተርፖል እንደገለጸው፣ በብዛት ለጥቃት የሚጋለጡት ያልተዘመኑ የሶፍትዌር ስርዓቶች፣ ለህዝብ የተጋለጡ የVPN አገልግሎቶች እና በትክክል ያልተዋቀሩ የሰነድ አስተዳደር መድረኮች ናቸው። እንዲሁም ኢትዮጵያ 1.36 በመቶ የአፍሪካ የቦትኔት ኖዶችን እንደምታስተናግድ ተገልጿል።
በተጨማሪም በሰው ሠራሽ የማሰብ ችሎታ (AI) የሚደገፍ ዲጂታል የጾታ ማስፈራሪያ (Sextortion) እያደገ የመጣ ስጋት ሲሆን፣ ኢትዮጵያ በዚህ ዘርፍ 8 በመቶ የአህጉራዊ መለኪያ ድርሻ እንዳላት ተጠቅሷል።
ሪፖርቱ በአፍሪካ ያሉ የህግ አስከባሪ ተቋማትም ከባድ የአቅም ችግሮች እንደሚያጋጥሟቸው ያመለክታል። 94 በመቶ የሚሆኑት ተቋማት በቂ የዲጂታል ፎረንሲክስ መሳሪያዎች እንደሌላቸው ሲገልጹ፣ 78 በመቶ የበጀትና የባለሙያ እጥረት እንዳለባቸው፣ 89 በመቶዎቹ ደግሞ በሀገራት መካከል የተሻለ ትብብር አለመኖሩ ዋና ተግዳሮት መሆኑን ጠቁመዋል።
በመጨረሻም ኢንተርፖልና የሳይበር ደህንነት ባለሙያዎች መንግስታት ድንበር ተሻጋሪ ትብብርን ማጠናከር፣ የሳይበር ንፅህና መርሆችን ማሻሻል፣ የመንግስትና የግል ዘርፍ አጋርነትን ማሳደግ እንዲሁም ዘመናዊ የህግ ማዕቀፎችን ማዘጋጀት ወሳኝ መሆኑን አሳስበዋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
21 hours ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) ጃኬን አሳታሚ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር ባለፉት ጥቂት ቀናት ውስጥ በድርጅቱ፣ በሰራተኞቹ እና በንብረቶቹ ላይ የተፈጸሙ ተከታታይ እና ከባድ ጥቃቶችን አስመልክቶ ለአጋሮቹ፣ ለዲፕሎማቲክ ማህበረሰቡ፣ ለሰብአዊ መብት ተሟጋቾች እና ለመላው ህዝብ ይፋዊ መግለጫ አውጥቷል።
በመግለጫው መሰረት ቅዳሜ ኦገስት 1 ቀን 2026 የ'አዲስ ስታንዳርድ' ዋና አዘጋጅ የሆነው ዮናስ ከድር በጸጥታ ኃይሎች ታፍኖ ከተወሰደ በኋላ ለ24 ሰዓታት ያህል አካላዊ ጥቃት እና የተራዘመ ምርመራ ተፈጽሞበታል። ዋና አዘጋጁ ከተለቀቀ በኋላ በደረሰበት ጥቃት ዙሪያ ዝርዝር የጽሁፍ ሪፖርት ለድርጅቱ የህግ ክፍል ያቀረበ ሲሆን፣ ይህም ማስረጃ ለቀጣይ የህግ ሂደት አካል ሆኖ መያዙን አሳታሚው ገልጿል።
በማግስቱ እሁድ ኦገስት 2 ቀን 2026 ደግሞ ከባድ መሳሪያ የታጠቁ የጸጥታ እና የደህንነት ኃይሎች ያለምንም ህጋዊ ሂደት ወደ አዲስ ስታንዳርድ ቢሮ በመግባት በልዩ ሁኔታ ከተገነባው የፕሮዳክሽን ስቱዲዮ ውስጥ ከፍተኛ መጠን ያላቸውን የመልቲሚዲያ እቃዎች ወስደዋል። ከጥቃቱ በኋላ የድርጅቱ የሰው ሀብት አስተዳደር እና የህንፃው አስተዳደር ባደረጉት ማጣራት፣ በርካታ ፕሮፌሽናል 4K የቪዲዮ ካሜራዎች፣ ትሪፖዶች፣ የድምፅ መቅረጫ መሳሪያዎች እና ሌሎች ለስራው እጅግ አስፈላጊ የሆኑ የብሮድካስት ግብዓቶች መወሰዳቸውን አረጋግጠዋል። በተጨማሪም በስቱዲዮው የብርሃን ስርዓቶች እና በተያያዥ መሳሪያዎች ላይ ሆን ተብሎ የተፈጸመ የውድመት ድርጊት መስተዋሉን አሳታሚው ጠቁሟል። የጠፉት እና የወደሙት ንብረቶች ሙሉ ዝርዝር እና ግምት ለህግ ሂደት እንዲያገለግል ተሰንዶ ተቀምጧል።
በድርጅቱ ላይ ያለው ጫና ይበልጥ ተባብሶ ሰኞ ኦገስት 3 ቀን 2026፣ ጃኬን አሳታሚ ላለፉት 16 ዓመታት ሲሰራበት የነበረው ህንፃ አስተዳደር በፖሊስ በተደረገበት ጫና ምክንያት ኩባንያው በሶስት ቀናት ውስጥ ቢሮውን ለቆ እንዲወጣ የማስጠንቀቂያ ደብዳቤ እንዲሰጥ ተገዷል። ሆኖም የጃኬን የህግ ክፍል ይህ የማስወጣት እርምጃ ህጋዊ የውል መሰረት የሌለው እና አስገዳጅ የሆነውን የኪራይ ውል የሚጥስ መሆኑን በመግለጽ ማስጠንቀቂያውን ለመቃወም ህጋዊ እርምጃ መጀመሩን አስታውቋል።
እነዚህ ተከታታይ ክስተቶች የተፈጸሙት ጃኬን አሳታሚ የኢትዮጵያ ሚዲያ ባለስልጣን የ'አዲስ ስታንዳርድ'ን የኦንላይን ሚዲያ ምዝገባ ፈቃድ ለመሰረዝ ያሳለፈውን ውሳኔ በመቃወም ፍርድ ቤት ባቀረበው አቤቱታ ላይ የህግ ክትትል እያደረገ ባለበት ወቅት ነው። ይህ የድርጊቶች ቅደም ተከተል ነጻ የሚዲያ ተቋማት ከማስፈራራት እና ከህገ-ወጥ ጣልቃ ገብነት ነጻ ሆነው ለመስራት ያላቸውን አቅም፣ እንዲሁም የህግ የበላይነት መኖር ላይ ጥልቅ ስጋት የሚፈጥር ነው ሲል ድርጅቱ ገልጿል።
ጃኬን አሳታሚ የፍትህ ሚኒስቴር፣ የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ እና የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን የድርጅቱ የህግ ክፍል በሚያደርገው ማጣራት ላይ ሙሉ ትብብር እንዲያደርጉ፣ የተወሰደው እርምጃ ህጋዊ መሰረት እንዲገለጽ እና ተጠያቂነት እንዲሰፍን ጥሪ አቅርቧል። እንዲሁም የሀገሪቱ የፍትህ ተቋማት የህግ ሂደትን እንዲያከብሩ እና በህገ-መንግስቱ የተረጋገጠውን የሀሳብን በነጻነት የመግለጽ፣ የፕሬስ ነጻነት እና የህግ የበላይነት መብቶችን እንዲያስጠብቁ አሳስቧል።
ጃኬን አሳታሚ ኃ/የተ/የግ/ማህበር እና አዲስ ስታንዳርድ ሚዲያ ይህ ሁሉ ያልተጠበቀ ፈታኝ ሁኔታ ቢኖርም፣ ለነጻ፣ ሙያዊ እና የህዝብን ጥቅም ለሚያስቀድም የጋዜጠኝነት ስራ ያላቸውን ቁርጠኝነት አጠናክረው እንደሚቀጥሉ አረጋግጠዋል። ድርጅቱም የሰራተኞቹን ደህንነት ለመጠበቅ እና መብቱን ለማስከበር ሁሉንም ህጋዊ አማራጮች እንደሚጠቀም አስታውቋል።
በመግለጫው መሰረት ቅዳሜ ኦገስት 1 ቀን 2026 የ'አዲስ ስታንዳርድ' ዋና አዘጋጅ የሆነው ዮናስ ከድር በጸጥታ ኃይሎች ታፍኖ ከተወሰደ በኋላ ለ24 ሰዓታት ያህል አካላዊ ጥቃት እና የተራዘመ ምርመራ ተፈጽሞበታል። ዋና አዘጋጁ ከተለቀቀ በኋላ በደረሰበት ጥቃት ዙሪያ ዝርዝር የጽሁፍ ሪፖርት ለድርጅቱ የህግ ክፍል ያቀረበ ሲሆን፣ ይህም ማስረጃ ለቀጣይ የህግ ሂደት አካል ሆኖ መያዙን አሳታሚው ገልጿል።
በማግስቱ እሁድ ኦገስት 2 ቀን 2026 ደግሞ ከባድ መሳሪያ የታጠቁ የጸጥታ እና የደህንነት ኃይሎች ያለምንም ህጋዊ ሂደት ወደ አዲስ ስታንዳርድ ቢሮ በመግባት በልዩ ሁኔታ ከተገነባው የፕሮዳክሽን ስቱዲዮ ውስጥ ከፍተኛ መጠን ያላቸውን የመልቲሚዲያ እቃዎች ወስደዋል። ከጥቃቱ በኋላ የድርጅቱ የሰው ሀብት አስተዳደር እና የህንፃው አስተዳደር ባደረጉት ማጣራት፣ በርካታ ፕሮፌሽናል 4K የቪዲዮ ካሜራዎች፣ ትሪፖዶች፣ የድምፅ መቅረጫ መሳሪያዎች እና ሌሎች ለስራው እጅግ አስፈላጊ የሆኑ የብሮድካስት ግብዓቶች መወሰዳቸውን አረጋግጠዋል። በተጨማሪም በስቱዲዮው የብርሃን ስርዓቶች እና በተያያዥ መሳሪያዎች ላይ ሆን ተብሎ የተፈጸመ የውድመት ድርጊት መስተዋሉን አሳታሚው ጠቁሟል። የጠፉት እና የወደሙት ንብረቶች ሙሉ ዝርዝር እና ግምት ለህግ ሂደት እንዲያገለግል ተሰንዶ ተቀምጧል።
በድርጅቱ ላይ ያለው ጫና ይበልጥ ተባብሶ ሰኞ ኦገስት 3 ቀን 2026፣ ጃኬን አሳታሚ ላለፉት 16 ዓመታት ሲሰራበት የነበረው ህንፃ አስተዳደር በፖሊስ በተደረገበት ጫና ምክንያት ኩባንያው በሶስት ቀናት ውስጥ ቢሮውን ለቆ እንዲወጣ የማስጠንቀቂያ ደብዳቤ እንዲሰጥ ተገዷል። ሆኖም የጃኬን የህግ ክፍል ይህ የማስወጣት እርምጃ ህጋዊ የውል መሰረት የሌለው እና አስገዳጅ የሆነውን የኪራይ ውል የሚጥስ መሆኑን በመግለጽ ማስጠንቀቂያውን ለመቃወም ህጋዊ እርምጃ መጀመሩን አስታውቋል።
እነዚህ ተከታታይ ክስተቶች የተፈጸሙት ጃኬን አሳታሚ የኢትዮጵያ ሚዲያ ባለስልጣን የ'አዲስ ስታንዳርድ'ን የኦንላይን ሚዲያ ምዝገባ ፈቃድ ለመሰረዝ ያሳለፈውን ውሳኔ በመቃወም ፍርድ ቤት ባቀረበው አቤቱታ ላይ የህግ ክትትል እያደረገ ባለበት ወቅት ነው። ይህ የድርጊቶች ቅደም ተከተል ነጻ የሚዲያ ተቋማት ከማስፈራራት እና ከህገ-ወጥ ጣልቃ ገብነት ነጻ ሆነው ለመስራት ያላቸውን አቅም፣ እንዲሁም የህግ የበላይነት መኖር ላይ ጥልቅ ስጋት የሚፈጥር ነው ሲል ድርጅቱ ገልጿል።
ጃኬን አሳታሚ የፍትህ ሚኒስቴር፣ የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ እና የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን የድርጅቱ የህግ ክፍል በሚያደርገው ማጣራት ላይ ሙሉ ትብብር እንዲያደርጉ፣ የተወሰደው እርምጃ ህጋዊ መሰረት እንዲገለጽ እና ተጠያቂነት እንዲሰፍን ጥሪ አቅርቧል። እንዲሁም የሀገሪቱ የፍትህ ተቋማት የህግ ሂደትን እንዲያከብሩ እና በህገ-መንግስቱ የተረጋገጠውን የሀሳብን በነጻነት የመግለጽ፣ የፕሬስ ነጻነት እና የህግ የበላይነት መብቶችን እንዲያስጠብቁ አሳስቧል።
ጃኬን አሳታሚ ኃ/የተ/የግ/ማህበር እና አዲስ ስታንዳርድ ሚዲያ ይህ ሁሉ ያልተጠበቀ ፈታኝ ሁኔታ ቢኖርም፣ ለነጻ፣ ሙያዊ እና የህዝብን ጥቅም ለሚያስቀድም የጋዜጠኝነት ስራ ያላቸውን ቁርጠኝነት አጠናክረው እንደሚቀጥሉ አረጋግጠዋል። ድርጅቱም የሰራተኞቹን ደህንነት ለመጠበቅ እና መብቱን ለማስከበር ሁሉንም ህጋዊ አማራጮች እንደሚጠቀም አስታውቋል።
22 hours ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ የጉምሩክ ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር የሆኑትን አቶ አዘዘው ጫኔን በቁጥጥር ስር ማዋሉን አስታወቀ። ዜናው የሀገሪቱን የፋይናንስ እና የጸጥታ ተቋማት በእጅጉ ያስገረመ ሲሆን፣ ምክትል ኮሚሽነሩ በቁጥጥር ስር የዋሉት "ህገ-ወጥ ንግድን እና የኮንትሮባንድ ዝውውርን ይቆጣጠራሉ" ተብሎ በተሰጣቸው ከፍተኛ የኃላፊነት ወንበር ላይ ተቀምጠው፣ በተቃራኒው መንግስትን ለከፍተኛ ኪሳራ የዳረገ የተደራጀ ወንጀል ፈጽመዋል በሚል ነው።
አቶ አዘዘው ጫኔ የጉምሩክ ኮሚሽን የህግ ተገዥነት ዘርፍ ምክትል ኮሚሽነር ሆነው ሲያገለግሉ የቆዩ ቢሆንም፣ አሁን ላይ ግን ሀገርን ከኢኮኖሚ አሻጥር ከመጠበቅ ይልቅ አሻጥሩን በዋናነት ሲመሩት እንደነበር ፖሊስ አስታውቋል። ዘ-ሐበሻ የተመለከተው በምክትል ኮሚሽነሩ ላይ ከቀረቡት ዋና ዋና የጥርጣሬ ክሶች መካከል በገቢዎች እና ጉምሩክ አስተዳደር ውስጥ የዘረጉትን ሰፊ መረብ በመጠቀም፣ ትክክለኛ የግብር ምዘናዎችን በማዛባት እና መንግስት ማግኘት የነበረበትን ከፍተኛ ገቢ በማሳጣት የግብር ምዘና ማጭበርበር ወንጀል መፈጸማቸው በዋናነት ይጠቀሳል። ከዚህም በተጨማሪ የሐሰት የክፍያ ደረሰኞችን እና ህገ-ወጥ ሰነዶችን ወደ ተቋሙ ስርዓት በማስገባት እና በማስተናገድ የሰነድ ማጭበርበር እንደፈጸሙ ተገልጿል።
በተያያዘም የመንግሥትን ገቢ ለመቀነስ፣ የፈጸሙትን ወንጀል ዱካ ለማጥፋት እና ምርመራን ለማደናቀፍ ሲባል የተቋሙን ቁልፍ የኮምፒውተር መረጃዎች ሆን ብሎ በመደምሰስ የኤሌክትሮኒክስ መረጃዎችን በማጥፋት ክስ ቀርቦባቸዋል። ከዚህ ሁሉ ባለፈ፣ አሁን ላይ ሀገሪቱ ተግባራዊ እያደረገች ያለውን የማክሮ-ኢኮኖሚ ማሻሻያ ፕሮግራም ለማስተጓጎል በማሰብ፣ ከኮንትሮባንድ አዘዋዋሪዎች እና ከሌሎች ህገ-ወጥ የጥቅም መረቦች ጋር በቀጥታ በመመሳጠር የተደራጀ የኢኮኖሚ አሻጥር መፈጸማቸው በምርመራ መመላከቱን ፖሊስ አብራርቷል።
ይህ ክስተት የህግ የበላይነትን እና የተቋማት ታማኝነትን በተመለከተ ትልቅ ጥያቄ የሚያስነሳ ነው። የህግ ተገዥነትን እንዲያስከብሩ የተሾሙ ከፍተኛ ባለስልጣን፣ የመንግስትን የኤሌክትሮኒክስ መረጃዎች እስከማጥፋት እና ከኮንትሮባንዲስቶች ጋር እስከመመሳጠር መድረሳቸው በጉምሩክ ኮሚሽኑ የውስጥ ቁጥጥር ስርዓት ላይ ትልቅ የደህንነት ክፍተት መኖሩን ፍንትው አድርጎ ያሳያል።
በተለይም መንግስት የማክሮ-ኢኮኖሚ ማሻሻያውን ተከትሎ የውጭ ምንዛሬ እና የገበያ መረጋጋትን ለማምጣት በሚጥርበት በዚህ ወሳኝ ወቅት፣ ቁልፍ የተቋሙ አመራሮች ራሳቸው ስርዓቱን ለማፍረስ በሚደረግ አሻጥር ውስጥ መገኘታቸው፣ የጸረ-ሙስና ዘመቻው ከመቼውም ጊዜ በላይ ከራሱ ከመንግስት መዋቅር መጀመር እንዳለበት የሚያመላክት ነው። ፌዴራል ፖሊስ በጉዳዩ ላይ የጀመረውን ጥልቅ ምርመራ አጠናክሮ መቀጠሉን ገልጿል።
አቶ አዘዘው ጫኔ የጉምሩክ ኮሚሽን የህግ ተገዥነት ዘርፍ ምክትል ኮሚሽነር ሆነው ሲያገለግሉ የቆዩ ቢሆንም፣ አሁን ላይ ግን ሀገርን ከኢኮኖሚ አሻጥር ከመጠበቅ ይልቅ አሻጥሩን በዋናነት ሲመሩት እንደነበር ፖሊስ አስታውቋል። ዘ-ሐበሻ የተመለከተው በምክትል ኮሚሽነሩ ላይ ከቀረቡት ዋና ዋና የጥርጣሬ ክሶች መካከል በገቢዎች እና ጉምሩክ አስተዳደር ውስጥ የዘረጉትን ሰፊ መረብ በመጠቀም፣ ትክክለኛ የግብር ምዘናዎችን በማዛባት እና መንግስት ማግኘት የነበረበትን ከፍተኛ ገቢ በማሳጣት የግብር ምዘና ማጭበርበር ወንጀል መፈጸማቸው በዋናነት ይጠቀሳል። ከዚህም በተጨማሪ የሐሰት የክፍያ ደረሰኞችን እና ህገ-ወጥ ሰነዶችን ወደ ተቋሙ ስርዓት በማስገባት እና በማስተናገድ የሰነድ ማጭበርበር እንደፈጸሙ ተገልጿል።
በተያያዘም የመንግሥትን ገቢ ለመቀነስ፣ የፈጸሙትን ወንጀል ዱካ ለማጥፋት እና ምርመራን ለማደናቀፍ ሲባል የተቋሙን ቁልፍ የኮምፒውተር መረጃዎች ሆን ብሎ በመደምሰስ የኤሌክትሮኒክስ መረጃዎችን በማጥፋት ክስ ቀርቦባቸዋል። ከዚህ ሁሉ ባለፈ፣ አሁን ላይ ሀገሪቱ ተግባራዊ እያደረገች ያለውን የማክሮ-ኢኮኖሚ ማሻሻያ ፕሮግራም ለማስተጓጎል በማሰብ፣ ከኮንትሮባንድ አዘዋዋሪዎች እና ከሌሎች ህገ-ወጥ የጥቅም መረቦች ጋር በቀጥታ በመመሳጠር የተደራጀ የኢኮኖሚ አሻጥር መፈጸማቸው በምርመራ መመላከቱን ፖሊስ አብራርቷል።
ይህ ክስተት የህግ የበላይነትን እና የተቋማት ታማኝነትን በተመለከተ ትልቅ ጥያቄ የሚያስነሳ ነው። የህግ ተገዥነትን እንዲያስከብሩ የተሾሙ ከፍተኛ ባለስልጣን፣ የመንግስትን የኤሌክትሮኒክስ መረጃዎች እስከማጥፋት እና ከኮንትሮባንዲስቶች ጋር እስከመመሳጠር መድረሳቸው በጉምሩክ ኮሚሽኑ የውስጥ ቁጥጥር ስርዓት ላይ ትልቅ የደህንነት ክፍተት መኖሩን ፍንትው አድርጎ ያሳያል።
በተለይም መንግስት የማክሮ-ኢኮኖሚ ማሻሻያውን ተከትሎ የውጭ ምንዛሬ እና የገበያ መረጋጋትን ለማምጣት በሚጥርበት በዚህ ወሳኝ ወቅት፣ ቁልፍ የተቋሙ አመራሮች ራሳቸው ስርዓቱን ለማፍረስ በሚደረግ አሻጥር ውስጥ መገኘታቸው፣ የጸረ-ሙስና ዘመቻው ከመቼውም ጊዜ በላይ ከራሱ ከመንግስት መዋቅር መጀመር እንዳለበት የሚያመላክት ነው። ፌዴራል ፖሊስ በጉዳዩ ላይ የጀመረውን ጥልቅ ምርመራ አጠናክሮ መቀጠሉን ገልጿል።
1 day ago
መንግሥት ሌብነትን እና ሕገወጥነትን ለመከላከል ጠንካራ እርምጃ እየወሰደ መሆኑን ገለጸ
በኢትዮጵያ ተግባራዊ እየተደረገ ያለውን ሰፊ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ለማደናቀፍ በሚንቀሳቀሱ እና የሀገር ሀብት በሚመዘብሩ አካላት ላይ መንግሥት የማያዳግም እርምጃ እየወሰደ መሆኑን አስታወቀ።
የኢፌዴሪ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ወይዘሮ እናትዓለም መለሰ ዛሬ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ፤ ኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት ፈጣን ልማትና ዕድገት እንድታረጋግጥ በርካታ ሥራዎች መሠራታቸውን ጠቅሰው፣ በዚህም ሰፋፊና አስደናቂ ሀገራዊ ውጤቶች መመዝገባቸውን ገልጸዋል፡፡ በዚህ ሂደት ግን ይህ ውጤት ጉዞው አልጋ በአልጋ እንዳልነበር አመላክተዋል ። ከተለያዩ ሀገራዊና ዓለም አቀፋዊ ተግዳሮቶች ባሻገር፣ ሕገ-ወጥነት እና የሙስና ተግባራት የልማቱ ዋነኛ ፈተና ሆነው መቆየታቸውንም ክብርት ሚኒስትሯ አብራርተዋል።
እንደ ሚኒስትሯ ገለጻ፣ የሕገ-ወጥነት ችግር በአንድ ወገን ብቻ የሚፈጸም ሳይሆን በርካታ የኅብረተሰብ ክፍሎችን የሚያጠቃልል መሆኑን ገልጸው ከውስጥም ከውጪም ያሉ በርካታ ኃይሎች በተደራጀ መንገድ ሲንቀሳቀሱ ነበር፡፡ በንግዱ ማኅበረሰብ፣ በልማት ድርጅቶች፣ በመንግሥት መዋቅር፣ በግለሰቦች እና በተገልጋዮች ጭምር በተደራጀ መንገድ በስፋት የሚታይ ነው።
እነዚህ አካላት ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያውን ከቁጥጥር ውጭ ለማድረግ በፋይናንስ እና በንግድ ሥርዐቱ ውስጥ ሰርገው በመግባት ከፍተኛ የኢኮኖሚ አሻጥር ሲፈጽሙ ቆይተዋል" ያሉት ወይዘሮ እናትዓለም፤ ድርጊቱ ሀገሪቱ የውጭ ምንዛሬ እንድታጣ፣ የዋጋ ንረትና ኮንትሮባንድ እንዲባባስ እንዲሁም በፍጆታ እቃዎች ላይ ሰው ሠራሽ እጥረት እንዲፈጠር ማድረጉን አስታውቀዋል። ይህንን የተደራጀ አሻጥር ለመግታት መንግሥት እና የሚመለከታቸው የሕግ አካላት ባከናወኑት ሰፊ ኦፕሬሽን አሻጥሩን ማክሸፍ መቻሉ ተገልጿል።
በሌላ በኩል በመንግሥት አገልግሎት ሰጪ እና አስተዳደር አካላት እንዲሁም የሕዝብ ተቋማት ውስጥ የተሰገሰጉ ሌቦችን በማጽዳት ረገድ መንግሥት ቁርጠኛ እርምጃ እየወሰደ እንደሚገኝ ያስታወቁት ወ/ሮ እናትዓለም በሕዝብ ሀብት ላይ ከፍተኛ ምዝበራ የፈጸሙ እና ተቋማዊ አሻጥር በሠሩ አመራሮች እና ሌሎች የጥቅም ትስስሮችና ድርጅቶች ላይ የማያዳግም እርምጃ መወሰዱንም አስታውቀዋል። በተለይም በሚከተሉት ቁልፍ ዘርፎች ላይ በተፈጸሙ ወንጀሎች ሰፊ ማጣራት ተደርጎ ተጠያቂነት ሰፍኗል ሲሉ ገልጸዋል፡
በመንግሥት አገልግሎት ሰጪ እና አስተዳደር አካላት፣ እንዲሁም ልዩ ልዩ የልማት ዘርፎች ውስጥ የተፈጸሙ ዋና ዋና የሙስና እና አሻጥር ወንጀሎችን ለማረም በተወሰዱት ሰፊ ኦፕሬሽኖች እና ሕግ የማስከበር እርምጃዎች ተጨባጭ ውጤቶች ተመዝግበዋል። ከማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ጋር በተያያዘ ማሻሻያውን ለማደናቀፍ በማሰብ መሠረታዊ የፍጆታ ምርቶችን በማከማቸት እጥረት እንዲፈጠርና ዋጋ እንዲንር ሲያደርጉ የነበሩ 13 አቅራቢ ድርጅቶች ባለቤቶች ላይ ማስጠንቀቂያ ተሰጥቷል፤ ሕገ-ወጥ ተግባር ሲፈጽሙ በነበሩ ከ7 ሺህ በላይ የንግድ ድርጅቶችና መጋዘኖች ላይ የማሸግ እርምጃ ተወስዷል።
በፋይናንስ ተቋማት እና የገንዘብ ዝውውር፡ በሕገ-ወጥ የገንዘብ ዝውውር፣ በሐዋላ እና በጥቁር ገበያ ተሳታፊ የሆኑ 169 ኢትዮጵያውያንና የውጭ ሀገር ዜጎች በሕግ ተጠያቂ እንዲሆኑ ተደርጓል። በተደራጀ መንገድ ከንግድ ባንክ ደንበኞች አካውንት ላይ በማጭበርበር ገንዘብ የወሰዱ 36 ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ውለው የባንክ ሒሳባቸው እንዲታገድ ተደርጓል።
ለሕገ-ወጥ ዝውውር ሽፋን ይሰጡ የነበሩ 7 የክሪፕቶ ካረንሲ መተግበሪያዎች በሀገር ውስጥ እንዳይሠሩ ሙሉ በሙሉ ታግደዋል፤ ምርት ልከው የውጭ ምንዛሬ ተመላሽ ያላደረጉ 29 ላኪ የንግድ ድርጅቶችና ግለሰቦች ላይም የህግ ተጠያቂነት ሰፍኗል።
በቤቲንግ እና ፊንቴክ ቢዝነሶች፡ የደንበኞችን መረጃ በመደበቅ መንግሥትን ግብር ያጭበረበሩ፣ ገቢያቸውን የሰወሩ እና ሕገ-ወጥ የገንዘብ ዝውውር በፈጸሙ 38 የቤቲንግ ድርጅቶች ላይ እርምጃ ተወስዶ ባለቤቶቻቸው በቁጥጥር ስር ውለዋል፤ የእነዚህ ሕገ-ወጥ ተቋማት የባንክ ሒሳብ ታግዷል፤
በማዕድን ዘርፍ ሕገ-ወጥ ዝውውር፡ የወርቅ ምርትን ከገበያ ውጭ በኮንትሮባንድ በማስወጣት ወንጀል የተሳተፉ የመንግሥት ኃላፊዎችን፣ የፀጥታ መዋቅር አመራሮችን፣ አምራቾችን እና የውጭ ዜጎችን ጨምሮ 183 ግለሰቦች በሕግ ተጠያቂ ተደርገዋል። በወንጀሉ የተሳተፉ የውጭ ሀገር ዜጎች ከሀገር እንዲወጡ ተደርገዋል፤ ሕገ-ወጥ ወርቅ፣ የወርቅ ሚዛንና ማቅለጫ፣ የተለያዩ የውጭ ሀገራት ገንዘቦች፣ እንዲሁም የጦር መሳሪያዎች በቁጥጥር ስር ውለዋል።
ከነዳጅ አቅርቦት እና ሎጂስቲክስ አንጻር፡ በሕገ-ወጥ መንገድ የሽፋን ደብዳቤዎችን በማዘጋጀት፣ ነዳጅ በመደበቅ እና አየር በአየር በመሸጥ ወንጀል የተሳተፉ 38 የመንግሥት አመራሮች በሕግ ተጠያቂ እንዲሆኑ ተደርጓል። በተጨማሪም በሀገር አቀፍ ደረጃ በሕገ-ወጥ የነዳጅ ንግድ ላይ የተሰማሩ ከ650 በላይ ግለሰቦች፣ ማደያዎች እና አቅራቢ ኩባንያዎች ላይ የህግ እርምጃ ተወስዷል።
በአፈር ማዳበሪያ ግዢ አሻጥር፡ በተቋሙ የጥቅም ትስስር በመፍጠር ጥራት የጎደለውና ጊዜው ያለፈበት የአፈር ማዳበሪያ ግዢ እንዲፈጸም በማድረግ ሆን ብለው ችግር በፈጠሩ የግብርና ሚኒስቴር አመራሮች ላይ የወንጀል ተጠያቂነት እርምጃ ተወስዷል።
በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል (EEP)፡ ተገቢው መመሪያ በሌለበት ሁኔታ ከ36 የዳታ ማይኒንግ ድርጅቶች ጋር ሕገ-ወጥ የኃይል ሽያጭ ውል የፈጸሙ 4 ከፍተኛ አመራሮች ላይ እርምጃ ተወስዷል። የኤሌክትሪክ ኃይል ስርቆት የፈጸሙ ድርጅቶች እና ግለሰቦችም እንዲሁ በሕግ እንዲጠየቁ ተደርጓል።
በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር እና የሰዎች ዝውውር የውጭ ሀገር የሥራ ስምሪት ሲስተምን በማዛባት እና ጉቦ በመቀበል ወንጀል የተሳተፉ 8 ከፍተኛ አመራሮችና ሠራተኞች በሕግ ቁጥጥር ስር ውለዋል። እንዲሁም በሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውር ላይ የተሰማሩ 44 ደላሎች እና አዘዋዋሪዎች በሕግ ቁጥጥር ስር ሲውሉ፣ ሕገ-ወጥ ፈቃድ የነበራቸው ተቋማት ሙሉ በሙሉ ታሽገዋል።
በገቢዎችና ጉምሩክ ዘርፍ፡ የግብር ውሳኔዎችን በመቀነስ፣ ሐሰተኛ ደረሰኞች በማወራረድ፣ እና በሲስተም መረጃ በማጥፋት የመንግሥት ገቢን ባሳጡ አካላት ላይ ኦፕሬሽን ተካሂዷል። በራሳቸው፣ በዘመድ እና በሹፌሮቻቸው አካውንት በመጠቀም የጥቅም ትስስር የፈጠሩ 109 ተጠርጣሪዎች ተለይተው ከእነዚህ መካከል 91 ግለሰቦች በሕግ ቁጥጥር ስር ውለዋል።
መንግሥት የልማት እንቅፋት የሆኑትን ሙስና እና ሌብነት እንደማንኛውም ፈተና በጽናት እየተጋፈጣቸው መሆኑን ሚኒስትሯ አረጋግጠዋል።
መንግሥት ሌብነትን ለማጥፋት ዘመናዊ አሠራሮችን በመዘርጋት እና በዲሲፕሊን የታነጸ አመራር ለመገንባት ቁርጠኛ ነው" ያሉት ወይዘሮ እናትዓለም፤ ሕዝቡ በስፋት የሚያነሣቸውን "ሌብነትን አስቁሙልን" ጥያቄዎች ለመመለስ የተጀመረዉ ጠንካራ እርምጃ ውጤታማ እንዲሆኑ ማኅበረሰቡ ሙስናን በማጋለጥ፣ ሕጋዊ መብቱን በመደለያ ባለመጠየቅ እና ከሕገወጦች ጋር ባለመተባበር ከመንግሥት ጎን በመቆም ሀገርን ከሕገወጥነትና ሙስና የመከላከል ታሪካዊ ኃላፊነቱን እንዲወጣ ጥሪ አቅርበዋል።
የኢፌዴሪ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት
በኢትዮጵያ ተግባራዊ እየተደረገ ያለውን ሰፊ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ለማደናቀፍ በሚንቀሳቀሱ እና የሀገር ሀብት በሚመዘብሩ አካላት ላይ መንግሥት የማያዳግም እርምጃ እየወሰደ መሆኑን አስታወቀ።
የኢፌዴሪ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ወይዘሮ እናትዓለም መለሰ ዛሬ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ፤ ኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት ፈጣን ልማትና ዕድገት እንድታረጋግጥ በርካታ ሥራዎች መሠራታቸውን ጠቅሰው፣ በዚህም ሰፋፊና አስደናቂ ሀገራዊ ውጤቶች መመዝገባቸውን ገልጸዋል፡፡ በዚህ ሂደት ግን ይህ ውጤት ጉዞው አልጋ በአልጋ እንዳልነበር አመላክተዋል ። ከተለያዩ ሀገራዊና ዓለም አቀፋዊ ተግዳሮቶች ባሻገር፣ ሕገ-ወጥነት እና የሙስና ተግባራት የልማቱ ዋነኛ ፈተና ሆነው መቆየታቸውንም ክብርት ሚኒስትሯ አብራርተዋል።
እንደ ሚኒስትሯ ገለጻ፣ የሕገ-ወጥነት ችግር በአንድ ወገን ብቻ የሚፈጸም ሳይሆን በርካታ የኅብረተሰብ ክፍሎችን የሚያጠቃልል መሆኑን ገልጸው ከውስጥም ከውጪም ያሉ በርካታ ኃይሎች በተደራጀ መንገድ ሲንቀሳቀሱ ነበር፡፡ በንግዱ ማኅበረሰብ፣ በልማት ድርጅቶች፣ በመንግሥት መዋቅር፣ በግለሰቦች እና በተገልጋዮች ጭምር በተደራጀ መንገድ በስፋት የሚታይ ነው።
እነዚህ አካላት ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያውን ከቁጥጥር ውጭ ለማድረግ በፋይናንስ እና በንግድ ሥርዐቱ ውስጥ ሰርገው በመግባት ከፍተኛ የኢኮኖሚ አሻጥር ሲፈጽሙ ቆይተዋል" ያሉት ወይዘሮ እናትዓለም፤ ድርጊቱ ሀገሪቱ የውጭ ምንዛሬ እንድታጣ፣ የዋጋ ንረትና ኮንትሮባንድ እንዲባባስ እንዲሁም በፍጆታ እቃዎች ላይ ሰው ሠራሽ እጥረት እንዲፈጠር ማድረጉን አስታውቀዋል። ይህንን የተደራጀ አሻጥር ለመግታት መንግሥት እና የሚመለከታቸው የሕግ አካላት ባከናወኑት ሰፊ ኦፕሬሽን አሻጥሩን ማክሸፍ መቻሉ ተገልጿል።
በሌላ በኩል በመንግሥት አገልግሎት ሰጪ እና አስተዳደር አካላት እንዲሁም የሕዝብ ተቋማት ውስጥ የተሰገሰጉ ሌቦችን በማጽዳት ረገድ መንግሥት ቁርጠኛ እርምጃ እየወሰደ እንደሚገኝ ያስታወቁት ወ/ሮ እናትዓለም በሕዝብ ሀብት ላይ ከፍተኛ ምዝበራ የፈጸሙ እና ተቋማዊ አሻጥር በሠሩ አመራሮች እና ሌሎች የጥቅም ትስስሮችና ድርጅቶች ላይ የማያዳግም እርምጃ መወሰዱንም አስታውቀዋል። በተለይም በሚከተሉት ቁልፍ ዘርፎች ላይ በተፈጸሙ ወንጀሎች ሰፊ ማጣራት ተደርጎ ተጠያቂነት ሰፍኗል ሲሉ ገልጸዋል፡
በመንግሥት አገልግሎት ሰጪ እና አስተዳደር አካላት፣ እንዲሁም ልዩ ልዩ የልማት ዘርፎች ውስጥ የተፈጸሙ ዋና ዋና የሙስና እና አሻጥር ወንጀሎችን ለማረም በተወሰዱት ሰፊ ኦፕሬሽኖች እና ሕግ የማስከበር እርምጃዎች ተጨባጭ ውጤቶች ተመዝግበዋል። ከማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ጋር በተያያዘ ማሻሻያውን ለማደናቀፍ በማሰብ መሠረታዊ የፍጆታ ምርቶችን በማከማቸት እጥረት እንዲፈጠርና ዋጋ እንዲንር ሲያደርጉ የነበሩ 13 አቅራቢ ድርጅቶች ባለቤቶች ላይ ማስጠንቀቂያ ተሰጥቷል፤ ሕገ-ወጥ ተግባር ሲፈጽሙ በነበሩ ከ7 ሺህ በላይ የንግድ ድርጅቶችና መጋዘኖች ላይ የማሸግ እርምጃ ተወስዷል።
በፋይናንስ ተቋማት እና የገንዘብ ዝውውር፡ በሕገ-ወጥ የገንዘብ ዝውውር፣ በሐዋላ እና በጥቁር ገበያ ተሳታፊ የሆኑ 169 ኢትዮጵያውያንና የውጭ ሀገር ዜጎች በሕግ ተጠያቂ እንዲሆኑ ተደርጓል። በተደራጀ መንገድ ከንግድ ባንክ ደንበኞች አካውንት ላይ በማጭበርበር ገንዘብ የወሰዱ 36 ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ውለው የባንክ ሒሳባቸው እንዲታገድ ተደርጓል።
ለሕገ-ወጥ ዝውውር ሽፋን ይሰጡ የነበሩ 7 የክሪፕቶ ካረንሲ መተግበሪያዎች በሀገር ውስጥ እንዳይሠሩ ሙሉ በሙሉ ታግደዋል፤ ምርት ልከው የውጭ ምንዛሬ ተመላሽ ያላደረጉ 29 ላኪ የንግድ ድርጅቶችና ግለሰቦች ላይም የህግ ተጠያቂነት ሰፍኗል።
በቤቲንግ እና ፊንቴክ ቢዝነሶች፡ የደንበኞችን መረጃ በመደበቅ መንግሥትን ግብር ያጭበረበሩ፣ ገቢያቸውን የሰወሩ እና ሕገ-ወጥ የገንዘብ ዝውውር በፈጸሙ 38 የቤቲንግ ድርጅቶች ላይ እርምጃ ተወስዶ ባለቤቶቻቸው በቁጥጥር ስር ውለዋል፤ የእነዚህ ሕገ-ወጥ ተቋማት የባንክ ሒሳብ ታግዷል፤
በማዕድን ዘርፍ ሕገ-ወጥ ዝውውር፡ የወርቅ ምርትን ከገበያ ውጭ በኮንትሮባንድ በማስወጣት ወንጀል የተሳተፉ የመንግሥት ኃላፊዎችን፣ የፀጥታ መዋቅር አመራሮችን፣ አምራቾችን እና የውጭ ዜጎችን ጨምሮ 183 ግለሰቦች በሕግ ተጠያቂ ተደርገዋል። በወንጀሉ የተሳተፉ የውጭ ሀገር ዜጎች ከሀገር እንዲወጡ ተደርገዋል፤ ሕገ-ወጥ ወርቅ፣ የወርቅ ሚዛንና ማቅለጫ፣ የተለያዩ የውጭ ሀገራት ገንዘቦች፣ እንዲሁም የጦር መሳሪያዎች በቁጥጥር ስር ውለዋል።
ከነዳጅ አቅርቦት እና ሎጂስቲክስ አንጻር፡ በሕገ-ወጥ መንገድ የሽፋን ደብዳቤዎችን በማዘጋጀት፣ ነዳጅ በመደበቅ እና አየር በአየር በመሸጥ ወንጀል የተሳተፉ 38 የመንግሥት አመራሮች በሕግ ተጠያቂ እንዲሆኑ ተደርጓል። በተጨማሪም በሀገር አቀፍ ደረጃ በሕገ-ወጥ የነዳጅ ንግድ ላይ የተሰማሩ ከ650 በላይ ግለሰቦች፣ ማደያዎች እና አቅራቢ ኩባንያዎች ላይ የህግ እርምጃ ተወስዷል።
በአፈር ማዳበሪያ ግዢ አሻጥር፡ በተቋሙ የጥቅም ትስስር በመፍጠር ጥራት የጎደለውና ጊዜው ያለፈበት የአፈር ማዳበሪያ ግዢ እንዲፈጸም በማድረግ ሆን ብለው ችግር በፈጠሩ የግብርና ሚኒስቴር አመራሮች ላይ የወንጀል ተጠያቂነት እርምጃ ተወስዷል።
በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል (EEP)፡ ተገቢው መመሪያ በሌለበት ሁኔታ ከ36 የዳታ ማይኒንግ ድርጅቶች ጋር ሕገ-ወጥ የኃይል ሽያጭ ውል የፈጸሙ 4 ከፍተኛ አመራሮች ላይ እርምጃ ተወስዷል። የኤሌክትሪክ ኃይል ስርቆት የፈጸሙ ድርጅቶች እና ግለሰቦችም እንዲሁ በሕግ እንዲጠየቁ ተደርጓል።
በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር እና የሰዎች ዝውውር የውጭ ሀገር የሥራ ስምሪት ሲስተምን በማዛባት እና ጉቦ በመቀበል ወንጀል የተሳተፉ 8 ከፍተኛ አመራሮችና ሠራተኞች በሕግ ቁጥጥር ስር ውለዋል። እንዲሁም በሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውር ላይ የተሰማሩ 44 ደላሎች እና አዘዋዋሪዎች በሕግ ቁጥጥር ስር ሲውሉ፣ ሕገ-ወጥ ፈቃድ የነበራቸው ተቋማት ሙሉ በሙሉ ታሽገዋል።
በገቢዎችና ጉምሩክ ዘርፍ፡ የግብር ውሳኔዎችን በመቀነስ፣ ሐሰተኛ ደረሰኞች በማወራረድ፣ እና በሲስተም መረጃ በማጥፋት የመንግሥት ገቢን ባሳጡ አካላት ላይ ኦፕሬሽን ተካሂዷል። በራሳቸው፣ በዘመድ እና በሹፌሮቻቸው አካውንት በመጠቀም የጥቅም ትስስር የፈጠሩ 109 ተጠርጣሪዎች ተለይተው ከእነዚህ መካከል 91 ግለሰቦች በሕግ ቁጥጥር ስር ውለዋል።
መንግሥት የልማት እንቅፋት የሆኑትን ሙስና እና ሌብነት እንደማንኛውም ፈተና በጽናት እየተጋፈጣቸው መሆኑን ሚኒስትሯ አረጋግጠዋል።
መንግሥት ሌብነትን ለማጥፋት ዘመናዊ አሠራሮችን በመዘርጋት እና በዲሲፕሊን የታነጸ አመራር ለመገንባት ቁርጠኛ ነው" ያሉት ወይዘሮ እናትዓለም፤ ሕዝቡ በስፋት የሚያነሣቸውን "ሌብነትን አስቁሙልን" ጥያቄዎች ለመመለስ የተጀመረዉ ጠንካራ እርምጃ ውጤታማ እንዲሆኑ ማኅበረሰቡ ሙስናን በማጋለጥ፣ ሕጋዊ መብቱን በመደለያ ባለመጠየቅ እና ከሕገወጦች ጋር ባለመተባበር ከመንግሥት ጎን በመቆም ሀገርን ከሕገወጥነትና ሙስና የመከላከል ታሪካዊ ኃላፊነቱን እንዲወጣ ጥሪ አቅርበዋል።
የኢፌዴሪ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት
Sponsored by
Surafel
1 day ago
በስለት እያስፈራሩ የሞባይል ስልክ የቀሙ 3 ወንጀል ፈፃሚዎች በእስራት ተቀጡ።
ሳሙኤል ደሳለኝ፣ ዮሴፍ መስፍን እና ዳግም አድነው የተባሉ ወንጀል ፈፃሚዎች ሐምሌ 6 ቀን 2018 ዓ/ም በኮልፌ ቀራኒዩ ክፍለ ከተማ ሁለት ሰዎችን በስለት በማስፈራራት ሞባይል ስልካቸውን ቀምተው ይሰወራሉ፡፡
ሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ/ም ወረዳ 7 ልዩ ቦታው አንፎ ሮም ሰፈር ተብሎ ከሚጠራ አካባቢ ተመሳሳይ ወንጀል ሲፈፅሙ በፖሊስ አባላት እጅ ከፍንጅ ተይዘዋል፡፡
የቤተል አካባቢ ፖሊስ መምሪያ አስፈላጊውን ምርመራ በማጣራት የምርመራ መዝገቡን ለአቃቤ ህግ በመላክ ክስ እንዲመሰረትባቸው ያደርጋል፡፡
የወንጀል ፈፃሚዎችን ጉዳይ ሲመለከት የቆየው የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ኮልፌ ቀራንዮ ምድብ ፈጣን የወንጀል ችሎት ሳሙኤል ደሳለኝ እና ዮሴፍ መስፍን በ4 አመት ዳግም አድነው በ2 አመት ፅኑ እስራት እንዲቀጡ ውሳኔ አስተላልፎባቸዋል።
Addis Ababa police
ሳሙኤል ደሳለኝ፣ ዮሴፍ መስፍን እና ዳግም አድነው የተባሉ ወንጀል ፈፃሚዎች ሐምሌ 6 ቀን 2018 ዓ/ም በኮልፌ ቀራኒዩ ክፍለ ከተማ ሁለት ሰዎችን በስለት በማስፈራራት ሞባይል ስልካቸውን ቀምተው ይሰወራሉ፡፡
ሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ/ም ወረዳ 7 ልዩ ቦታው አንፎ ሮም ሰፈር ተብሎ ከሚጠራ አካባቢ ተመሳሳይ ወንጀል ሲፈፅሙ በፖሊስ አባላት እጅ ከፍንጅ ተይዘዋል፡፡
የቤተል አካባቢ ፖሊስ መምሪያ አስፈላጊውን ምርመራ በማጣራት የምርመራ መዝገቡን ለአቃቤ ህግ በመላክ ክስ እንዲመሰረትባቸው ያደርጋል፡፡
የወንጀል ፈፃሚዎችን ጉዳይ ሲመለከት የቆየው የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ኮልፌ ቀራንዮ ምድብ ፈጣን የወንጀል ችሎት ሳሙኤል ደሳለኝ እና ዮሴፍ መስፍን በ4 አመት ዳግም አድነው በ2 አመት ፅኑ እስራት እንዲቀጡ ውሳኔ አስተላልፎባቸዋል።
Addis Ababa police
1 day ago
በሙስናና ሕገ-ወጥ አሠራር የተሳተፉ አካላት ላይ የሕግ እርምጃ ተወሰደ
በኢትዮጵያ ተግባራዊ እየተደረገ ያለውን ሰፊ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ለማደናቀፍ በሚንቀሳቀሱ እና የሀገር ሀብት በሚመዘብሩ አካላት ላይ መንግሥት የማያዳግም እርምጃ እየወሰደ መሆኑን አስታወቀ።
የኢፌዴሪ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ወይዘሮ እናትዓለም መለሰ ዛሬ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ፤ ኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት ፈጣን ልማትና ዕድገት እንድታረጋግጥ በርካታ ሥራዎች መሠራታቸውን ጠቅሰው፣ በዚህም ሰፋፊና አስደናቂ ሀገራዊ ውጤቶች መመዝገባቸውን ገልጸዋል። በዚህ ሂደት ግን ይህ ውጤት ጉዞው አልጋ በአልጋ እንዳልነበር አመላክተዋል። ከተለያዩ ሀገራዊና ዓለም አቀፋዊ ተግዳሮቶች ባሻገር፣ ሕገ-ወጥነት እና የሙስና ተግባራት የልማቱ ዋነኛ ፈተና ሆነው መቆየታቸውንም ክብርት ሚኒስትሯ አብራርተዋል።
እንደ ሚኒስትሯ ገለጻ፣ የሕገ-ወጥነት ችግር በአንድ ወገን ብቻ የሚፈጸም ሳይሆን በርካታ የኅብረተሰብ ክፍሎችን የሚያጠቃልል መሆኑን ገልጸው ከውስጥም ከውጪም ያሉ በርካታ ኃይሎች በተደራጀ መንገድ ሲንቀሳቀሱ ነበር። በንግዱ ማኅበረሰብ፣ በልማት ድርጅቶች፣ በመንግሥት መዋቅር፣ በግለሰቦች እና በተገልጋዮች ጭምር በተደራጀ መንገድ በስፋት የሚታይ ነው።
እነዚህ አካላት ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያውን ከቁጥጥር ውጭ ለማድረግ በፋይናንስ እና በንግድ ሥርዐቱ ውስጥ ሰርገው በመግባት ከፍተኛ የኢኮኖሚ አሻጥር ሲፈጽሙ ቆይተዋል" ያሉት ወይዘሮ እናትዓለም፤ ድርጊቱ ሀገሪቱ የውጭ ምንዛሬ እንድታጣ፣ የዋጋ ንረትና ኮንትሮባንድ እንዲባባስ እንዲሁም በፍጆታ እቃዎች ላይ ሰው ሠራሽ እጥረት እንዲፈጠር ማድረጉን አስታውቀዋል። ይህንን የተደራጀ አሻጥር ለመግታት መንግሥት እና የሚመለከታቸው የሕግ አካላት ባከናወኑት ሰፊ ኦፕሬሽን አሻጥሩን ማክሸፍ መቻሉ ተገልጿል።
በሌላ በኩል በመንግሥት አገልግሎት ሰጪ እና አስተዳደር አካላት እንዲሁም የሕዝብ ተቋማት ውስጥ የተሰገሰጉ ሌቦችን በማጽዳት ረገድ መንግሥት ቁርጠኛ እርምጃ እየወሰደ እንደሚገኝ ያስታወቁት ወ/ሮ እናትዓለም በሕዝብ ሀብት ላይ ከፍተኛ ምዝበራ የፈጸሙ እና ተቋማዊ አሻጥር በሠሩ አመራሮች እና ሌሎች የጥቅም ትስስሮችና ድርጅቶች ላይ የማያዳግም እርምጃ መወሰዱንም አስታውቀዋል። በተለይም በሚከተሉት ቁልፍ ዘርፎች ላይ በተፈጸሙ ወንጀሎች ሰፊ ማጣራት ተደርጎ ተጠያቂነት ሰፍኗል ሲሉ ገልጸዋል።
በመንግሥት አገልግሎት ሰጪ እና አስተዳደር አካላት፣ እንዲሁም ልዩ ልዩ የልማት ዘርፎች ውስጥ የተፈጸሙ ዋና ዋና የሙስና እና አሻጥር ወንጀሎችን ለማረም በተወሰዱት ሰፊ ኦፕሬሽኖች እና ሕግ የማስከበር እርምጃዎች ተጨባጭ ውጤቶች ተመዝግበዋል። ከማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ጋር በተያያዘ ማሻሻያውን ለማደናቀፍ በማሰብ መሠረታዊ የፍጆታ ምርቶችን በማከማቸት እጥረት እንዲፈጠርና ዋጋ እንዲንር ሲያደርጉ የነበሩ 13 አቅራቢ ድርጅቶች ባለቤቶች ላይ ማስጠንቀቂያ ተሰጥቷል፤ ሕገ-ወጥ ተግባር ሲፈጽሙ በነበሩ ከ7 ሺህ በላይ የንግድ ድርጅቶችና መጋዘኖች ላይ የማሸግ እርምጃ ተወስዷል።
በፋይናንስ ተቋማት እና የገንዘብ ዝውውር፡ በሕገ-ወጥ የገንዘብ ዝውውር፣ በሐዋላ እና በጥቁር ገበያ ተሳታፊ የሆኑ 169 ኢትዮጵያውያንና የውጭ ሀገር ዜጎች በሕግ ተጠያቂ እንዲሆኑ ተደርጓል። በተደራጀ መንገድ ከንግድ ባንክ ደንበኞች አካውንት ላይ በማጭበርበር ገንዘብ የወሰዱ 36 ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ውለው የባንክ ሒሳባቸው እንዲታገድ ተደርጓል።
ለሕገ-ወጥ ዝውውር ሽፋን ይሰጡ የነበሩ 7 የክሪፕቶ ካረንሲ መተግበሪያዎች በሀገር ውስጥ እንዳይሠሩ ሙሉ በሙሉ ታግደዋል፤ ምርት ልከው የውጭ ምንዛሬ ተመላሽ ያላደረጉ 29 ላኪ የንግድ ድርጅቶችና ግለሰቦች ላይም የህግ ተጠያቂነት ሰፍኗል።
በቤቲንግ እና ፊንቴክ ቢዝነሶች፡ የደንበኞችን መረጃ በመደበቅ መንግሥትን ግብር ያጭበረበሩ፣ ገቢያቸውን የሰወሩ እና ሕገ-ወጥ የገንዘብ ዝውውር በፈጸሙ 38 የቤቲንግ ድርጅቶች ላይ እርምጃ ተወስዶ ባለቤቶቻቸው በቁጥጥር ስር ውለዋል፤ የእነዚህ ሕገ-ወጥ ተቋማት የባንክ ሒሳብ ታግዷል፤
በማዕድን ዘርፍ ሕገ-ወጥ ዝውውር፡ የወርቅ ምርትን ከገበያ ውጭ በኮንትሮባንድ በማስወጣት ወንጀል የተሳተፉ የመንግሥት ኃላፊዎችን፣ የፀጥታ መዋቅር አመራሮችን፣ አምራቾችን እና የውጭ ዜጎችን ጨምሮ 183 ግለሰቦች በሕግ ተጠያቂ ተደርገዋል። በወንጀሉ የተሳተፉ የውጭ ሀገር ዜጎች ከሀገር እንዲወጡ ተደርገዋል፤ ሕገ-ወጥ ወርቅ፣ የወርቅ ሚዛንና ማቅለጫ፣ የተለያዩ የውጭ ሀገራት ገንዘቦች፣ እንዲሁም የጦር መሳሪያዎች በቁጥጥር ስር ውለዋል።
ከነዳጅ አቅርቦት እና ሎጂስቲክስ አንጻር፡ በሕገ-ወጥ መንገድ የሽፋን ደብዳቤዎችን በማዘጋጀት፣ ነዳጅ በመደበቅ እና አየር በአየር በመሸጥ ወንጀል የተሳተፉ 38 የመንግሥት አመራሮች በሕግ ተጠያቂ እንዲሆኑ ተደርጓል። በተጨማሪም በሀገር አቀፍ ደረጃ በሕገ-ወጥ የነዳጅ ንግድ ላይ የተሰማሩ ከ650 በላይ ግለሰቦች፣ ማደያዎች እና አቅራቢ ኩባንያዎች ላይ የህግ እርምጃ ተወስዷል።
በአፈር ማዳበሪያ ግዢ አሻጥር፡ በተቋሙ የጥቅም ትስስር በመፍጠር ጥራት የጎደለውና ጊዜው ያለፈበት የአፈር ማዳበሪያ ግዢ እንዲፈጸም በማድረግ ሆን ብለው ችግር በፈጠሩ የግብርና ሚኒስቴር አመራሮች ላይ የወንጀል ተጠያቂነት እርምጃ ተወስዷል።
በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል (EEP)፡ ተገቢው መመሪያ በሌለበት ሁኔታ ከ36 የዳታ ማይኒንግ ድርጅቶች ጋር ሕገ-ወጥ የኃይል ሽያጭ ውል የፈጸሙ 4 ከፍተኛ አመራሮች ላይ እርምጃ ተወስዷል። የኤሌክትሪክ ኃይል ስርቆት የፈጸሙ ድርጅቶች እና ግለሰቦችም እንዲሁ በሕግ እንዲጠየቁ ተደርጓል።
በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር እና የሰዎች ዝውውር የውጭ ሀገር የሥራ ስምሪት ሲስተምን በማዛባት እና ጉቦ በመቀበል ወንጀል የተሳተፉ 8 ከፍተኛ አመራሮችና ሠራተኞች በሕግ ቁጥጥር ስር ውለዋል። እንዲሁም በሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውር ላይ የተሰማሩ 44 ደላሎች እና አዘዋዋሪዎች በሕግ ቁጥጥር ስር ሲውሉ፣ ሕገ-ወጥ ፈቃድ የነበራቸው ተቋማት ሙሉ በሙሉ ታሽገዋል።
በገቢዎችና ጉምሩክ ዘርፍ፡ የግብር ውሳኔዎችን በመቀነስ፣ ሐሰተኛ ደረሰኞች በማወራረድ፣ እና በሲስተም መረጃ በማጥፋት የመንግሥት ገቢን ባሳጡ አካላት ላይ ኦፕሬሽን ተካሂዷል።
በራሳቸው፣ በዘመድ እና በሹፌሮቻቸው አካውንት በመጠቀም የጥቅም ትስስር የፈጠሩ 109 ተጠርጣሪዎች ተለይተው ከእነዚህ መካከል 91 ግለሰቦች በሕግ ቁጥጥር ስር ውለዋል።
መንግሥት የልማት እንቅፋት የሆኑትን ሙስና እና ሌብነት እንደማንኛውም ፈተና በጽናት እየተጋፈጣቸው መሆኑን ሚኒስትሯ አረጋግጠዋል።
መንግሥት ሌብነትን ለማጥፋት ዘመናዊ አሠራሮችን በመዘርጋት እና በዲሲፕሊን የታነጸ አመራር ለመገንባት ቁርጠኛ ነው" ያሉት ወይዘሮ እናትዓለም፤ ሕዝቡ በስፋት የሚያነሣቸውን "ሌብነትን አስቁሙልን" ጥያቄዎች ለመመለስ የተጀመረዉ ጠንካራ እርምጃ ውጤታማ እንዲሆኑ ማኅበረሰቡ ሙስናን በማጋለጥ፣ ሕጋዊ መብቱን በመደለያ ባለመጠየቅ እና ከሕገወጦች ጋር ባለመተባበር ከመንግሥት ጎን በመቆም ሀገርን ከሕገወጥነትና ሙስና የመከላከል ታሪካዊ ኃላፊነቱን እንዲወጣ ጥሪ አቅርበዋል።
Via EBC
በኢትዮጵያ ተግባራዊ እየተደረገ ያለውን ሰፊ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ለማደናቀፍ በሚንቀሳቀሱ እና የሀገር ሀብት በሚመዘብሩ አካላት ላይ መንግሥት የማያዳግም እርምጃ እየወሰደ መሆኑን አስታወቀ።
የኢፌዴሪ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ወይዘሮ እናትዓለም መለሰ ዛሬ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ፤ ኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት ፈጣን ልማትና ዕድገት እንድታረጋግጥ በርካታ ሥራዎች መሠራታቸውን ጠቅሰው፣ በዚህም ሰፋፊና አስደናቂ ሀገራዊ ውጤቶች መመዝገባቸውን ገልጸዋል። በዚህ ሂደት ግን ይህ ውጤት ጉዞው አልጋ በአልጋ እንዳልነበር አመላክተዋል። ከተለያዩ ሀገራዊና ዓለም አቀፋዊ ተግዳሮቶች ባሻገር፣ ሕገ-ወጥነት እና የሙስና ተግባራት የልማቱ ዋነኛ ፈተና ሆነው መቆየታቸውንም ክብርት ሚኒስትሯ አብራርተዋል።
እንደ ሚኒስትሯ ገለጻ፣ የሕገ-ወጥነት ችግር በአንድ ወገን ብቻ የሚፈጸም ሳይሆን በርካታ የኅብረተሰብ ክፍሎችን የሚያጠቃልል መሆኑን ገልጸው ከውስጥም ከውጪም ያሉ በርካታ ኃይሎች በተደራጀ መንገድ ሲንቀሳቀሱ ነበር። በንግዱ ማኅበረሰብ፣ በልማት ድርጅቶች፣ በመንግሥት መዋቅር፣ በግለሰቦች እና በተገልጋዮች ጭምር በተደራጀ መንገድ በስፋት የሚታይ ነው።
እነዚህ አካላት ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያውን ከቁጥጥር ውጭ ለማድረግ በፋይናንስ እና በንግድ ሥርዐቱ ውስጥ ሰርገው በመግባት ከፍተኛ የኢኮኖሚ አሻጥር ሲፈጽሙ ቆይተዋል" ያሉት ወይዘሮ እናትዓለም፤ ድርጊቱ ሀገሪቱ የውጭ ምንዛሬ እንድታጣ፣ የዋጋ ንረትና ኮንትሮባንድ እንዲባባስ እንዲሁም በፍጆታ እቃዎች ላይ ሰው ሠራሽ እጥረት እንዲፈጠር ማድረጉን አስታውቀዋል። ይህንን የተደራጀ አሻጥር ለመግታት መንግሥት እና የሚመለከታቸው የሕግ አካላት ባከናወኑት ሰፊ ኦፕሬሽን አሻጥሩን ማክሸፍ መቻሉ ተገልጿል።
በሌላ በኩል በመንግሥት አገልግሎት ሰጪ እና አስተዳደር አካላት እንዲሁም የሕዝብ ተቋማት ውስጥ የተሰገሰጉ ሌቦችን በማጽዳት ረገድ መንግሥት ቁርጠኛ እርምጃ እየወሰደ እንደሚገኝ ያስታወቁት ወ/ሮ እናትዓለም በሕዝብ ሀብት ላይ ከፍተኛ ምዝበራ የፈጸሙ እና ተቋማዊ አሻጥር በሠሩ አመራሮች እና ሌሎች የጥቅም ትስስሮችና ድርጅቶች ላይ የማያዳግም እርምጃ መወሰዱንም አስታውቀዋል። በተለይም በሚከተሉት ቁልፍ ዘርፎች ላይ በተፈጸሙ ወንጀሎች ሰፊ ማጣራት ተደርጎ ተጠያቂነት ሰፍኗል ሲሉ ገልጸዋል።
በመንግሥት አገልግሎት ሰጪ እና አስተዳደር አካላት፣ እንዲሁም ልዩ ልዩ የልማት ዘርፎች ውስጥ የተፈጸሙ ዋና ዋና የሙስና እና አሻጥር ወንጀሎችን ለማረም በተወሰዱት ሰፊ ኦፕሬሽኖች እና ሕግ የማስከበር እርምጃዎች ተጨባጭ ውጤቶች ተመዝግበዋል። ከማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ጋር በተያያዘ ማሻሻያውን ለማደናቀፍ በማሰብ መሠረታዊ የፍጆታ ምርቶችን በማከማቸት እጥረት እንዲፈጠርና ዋጋ እንዲንር ሲያደርጉ የነበሩ 13 አቅራቢ ድርጅቶች ባለቤቶች ላይ ማስጠንቀቂያ ተሰጥቷል፤ ሕገ-ወጥ ተግባር ሲፈጽሙ በነበሩ ከ7 ሺህ በላይ የንግድ ድርጅቶችና መጋዘኖች ላይ የማሸግ እርምጃ ተወስዷል።
በፋይናንስ ተቋማት እና የገንዘብ ዝውውር፡ በሕገ-ወጥ የገንዘብ ዝውውር፣ በሐዋላ እና በጥቁር ገበያ ተሳታፊ የሆኑ 169 ኢትዮጵያውያንና የውጭ ሀገር ዜጎች በሕግ ተጠያቂ እንዲሆኑ ተደርጓል። በተደራጀ መንገድ ከንግድ ባንክ ደንበኞች አካውንት ላይ በማጭበርበር ገንዘብ የወሰዱ 36 ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ውለው የባንክ ሒሳባቸው እንዲታገድ ተደርጓል።
ለሕገ-ወጥ ዝውውር ሽፋን ይሰጡ የነበሩ 7 የክሪፕቶ ካረንሲ መተግበሪያዎች በሀገር ውስጥ እንዳይሠሩ ሙሉ በሙሉ ታግደዋል፤ ምርት ልከው የውጭ ምንዛሬ ተመላሽ ያላደረጉ 29 ላኪ የንግድ ድርጅቶችና ግለሰቦች ላይም የህግ ተጠያቂነት ሰፍኗል።
በቤቲንግ እና ፊንቴክ ቢዝነሶች፡ የደንበኞችን መረጃ በመደበቅ መንግሥትን ግብር ያጭበረበሩ፣ ገቢያቸውን የሰወሩ እና ሕገ-ወጥ የገንዘብ ዝውውር በፈጸሙ 38 የቤቲንግ ድርጅቶች ላይ እርምጃ ተወስዶ ባለቤቶቻቸው በቁጥጥር ስር ውለዋል፤ የእነዚህ ሕገ-ወጥ ተቋማት የባንክ ሒሳብ ታግዷል፤
በማዕድን ዘርፍ ሕገ-ወጥ ዝውውር፡ የወርቅ ምርትን ከገበያ ውጭ በኮንትሮባንድ በማስወጣት ወንጀል የተሳተፉ የመንግሥት ኃላፊዎችን፣ የፀጥታ መዋቅር አመራሮችን፣ አምራቾችን እና የውጭ ዜጎችን ጨምሮ 183 ግለሰቦች በሕግ ተጠያቂ ተደርገዋል። በወንጀሉ የተሳተፉ የውጭ ሀገር ዜጎች ከሀገር እንዲወጡ ተደርገዋል፤ ሕገ-ወጥ ወርቅ፣ የወርቅ ሚዛንና ማቅለጫ፣ የተለያዩ የውጭ ሀገራት ገንዘቦች፣ እንዲሁም የጦር መሳሪያዎች በቁጥጥር ስር ውለዋል።
ከነዳጅ አቅርቦት እና ሎጂስቲክስ አንጻር፡ በሕገ-ወጥ መንገድ የሽፋን ደብዳቤዎችን በማዘጋጀት፣ ነዳጅ በመደበቅ እና አየር በአየር በመሸጥ ወንጀል የተሳተፉ 38 የመንግሥት አመራሮች በሕግ ተጠያቂ እንዲሆኑ ተደርጓል። በተጨማሪም በሀገር አቀፍ ደረጃ በሕገ-ወጥ የነዳጅ ንግድ ላይ የተሰማሩ ከ650 በላይ ግለሰቦች፣ ማደያዎች እና አቅራቢ ኩባንያዎች ላይ የህግ እርምጃ ተወስዷል።
በአፈር ማዳበሪያ ግዢ አሻጥር፡ በተቋሙ የጥቅም ትስስር በመፍጠር ጥራት የጎደለውና ጊዜው ያለፈበት የአፈር ማዳበሪያ ግዢ እንዲፈጸም በማድረግ ሆን ብለው ችግር በፈጠሩ የግብርና ሚኒስቴር አመራሮች ላይ የወንጀል ተጠያቂነት እርምጃ ተወስዷል።
በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል (EEP)፡ ተገቢው መመሪያ በሌለበት ሁኔታ ከ36 የዳታ ማይኒንግ ድርጅቶች ጋር ሕገ-ወጥ የኃይል ሽያጭ ውል የፈጸሙ 4 ከፍተኛ አመራሮች ላይ እርምጃ ተወስዷል። የኤሌክትሪክ ኃይል ስርቆት የፈጸሙ ድርጅቶች እና ግለሰቦችም እንዲሁ በሕግ እንዲጠየቁ ተደርጓል።
በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር እና የሰዎች ዝውውር የውጭ ሀገር የሥራ ስምሪት ሲስተምን በማዛባት እና ጉቦ በመቀበል ወንጀል የተሳተፉ 8 ከፍተኛ አመራሮችና ሠራተኞች በሕግ ቁጥጥር ስር ውለዋል። እንዲሁም በሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውር ላይ የተሰማሩ 44 ደላሎች እና አዘዋዋሪዎች በሕግ ቁጥጥር ስር ሲውሉ፣ ሕገ-ወጥ ፈቃድ የነበራቸው ተቋማት ሙሉ በሙሉ ታሽገዋል።
በገቢዎችና ጉምሩክ ዘርፍ፡ የግብር ውሳኔዎችን በመቀነስ፣ ሐሰተኛ ደረሰኞች በማወራረድ፣ እና በሲስተም መረጃ በማጥፋት የመንግሥት ገቢን ባሳጡ አካላት ላይ ኦፕሬሽን ተካሂዷል።
በራሳቸው፣ በዘመድ እና በሹፌሮቻቸው አካውንት በመጠቀም የጥቅም ትስስር የፈጠሩ 109 ተጠርጣሪዎች ተለይተው ከእነዚህ መካከል 91 ግለሰቦች በሕግ ቁጥጥር ስር ውለዋል።
መንግሥት የልማት እንቅፋት የሆኑትን ሙስና እና ሌብነት እንደማንኛውም ፈተና በጽናት እየተጋፈጣቸው መሆኑን ሚኒስትሯ አረጋግጠዋል።
መንግሥት ሌብነትን ለማጥፋት ዘመናዊ አሠራሮችን በመዘርጋት እና በዲሲፕሊን የታነጸ አመራር ለመገንባት ቁርጠኛ ነው" ያሉት ወይዘሮ እናትዓለም፤ ሕዝቡ በስፋት የሚያነሣቸውን "ሌብነትን አስቁሙልን" ጥያቄዎች ለመመለስ የተጀመረዉ ጠንካራ እርምጃ ውጤታማ እንዲሆኑ ማኅበረሰቡ ሙስናን በማጋለጥ፣ ሕጋዊ መብቱን በመደለያ ባለመጠየቅ እና ከሕገወጦች ጋር ባለመተባበር ከመንግሥት ጎን በመቆም ሀገርን ከሕገወጥነትና ሙስና የመከላከል ታሪካዊ ኃላፊነቱን እንዲወጣ ጥሪ አቅርበዋል።
Via EBC
1 day ago
በፃድቃኔ ማርያም ቤተክርስቲያን ፀበል በተከሰተ ድንገተኛ የመሬት መንሸራተት አደጋ ህይወቷ ያለፈው የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ተማሪ
#ethiopia | በድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ የ4ኛ ዓመት የህግ ትምህርት ተማሪ የሆነችው ተማሪ ሀብታሟ በቀለ ለእረፍት ወደ ቤተሰብ ከመሄዷ ቀድማ በፃድቃኔ ማርያም ቤተክርስቲያን ፀበል በመከታተል ላይ ሳለች በአካባቢው በተከሰተ ድንገተኛ የመሬት መንሸራተት አደጋ ሐምሌ 27 ቀን 2018 ዓ/ም ከዚህ አለም ድካም አርፋለች።
ተማሪ ሀብታሟ በትምህርቷ ካስመዘገበችው ከፍተኛ ውጤት ባሻገር፣ በመልካም ስነ ምግባሯ፣ በታታሪ ተማሪነቷ፣ በክፍል ውስጥ ተሳትፎዋና ተግባቢ ስብዕናዎቿ የምትታወቅ፤ በተለይ በምስለ ችሎት ውድድሮች በምታሳየው የላቀ ችሎታ እና ውጤት እንዲሁም ዩኒቨርሲቲው ለአካባቢው ማህበረሰብ በሚሰጠው የነፃ ህግ አገልግሎት ድጋፎች ዙሪያ በነበራት ተሳትፎ የምትታወቅ ተማሪያችን ነበረች፡፡
የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ማኔጅመንት በተማሪ ሀብታሟ በቀለ ድንገተኛ ህልፈተ ህይወት የተሰማውን ጥልቅ ሐዘን እየገለፀ ለተማሪዋ ቤተሰብ፣ ወዳጅ ዘመድ፣ እንዲሁም ለመላው የዩኒቨርሲቲያችን ማህበረሰብ መፅናናትን ይመኛል፡፡
ድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ
#ethiopia | በድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ የ4ኛ ዓመት የህግ ትምህርት ተማሪ የሆነችው ተማሪ ሀብታሟ በቀለ ለእረፍት ወደ ቤተሰብ ከመሄዷ ቀድማ በፃድቃኔ ማርያም ቤተክርስቲያን ፀበል በመከታተል ላይ ሳለች በአካባቢው በተከሰተ ድንገተኛ የመሬት መንሸራተት አደጋ ሐምሌ 27 ቀን 2018 ዓ/ም ከዚህ አለም ድካም አርፋለች።
ተማሪ ሀብታሟ በትምህርቷ ካስመዘገበችው ከፍተኛ ውጤት ባሻገር፣ በመልካም ስነ ምግባሯ፣ በታታሪ ተማሪነቷ፣ በክፍል ውስጥ ተሳትፎዋና ተግባቢ ስብዕናዎቿ የምትታወቅ፤ በተለይ በምስለ ችሎት ውድድሮች በምታሳየው የላቀ ችሎታ እና ውጤት እንዲሁም ዩኒቨርሲቲው ለአካባቢው ማህበረሰብ በሚሰጠው የነፃ ህግ አገልግሎት ድጋፎች ዙሪያ በነበራት ተሳትፎ የምትታወቅ ተማሪያችን ነበረች፡፡
የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ማኔጅመንት በተማሪ ሀብታሟ በቀለ ድንገተኛ ህልፈተ ህይወት የተሰማውን ጥልቅ ሐዘን እየገለፀ ለተማሪዋ ቤተሰብ፣ ወዳጅ ዘመድ፣ እንዲሁም ለመላው የዩኒቨርሲቲያችን ማህበረሰብ መፅናናትን ይመኛል፡፡
ድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ
1 day ago
የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ የህግ ተማሪ በድንገተኛ አደጋ ህይወቷ አለፈ
#fastmereja I በድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ የ4ኛ ዓመት የህግ ትምህርት ተማሪ የሆነችው ሀብታሟ በቀለ ለእረፍት ወደ ቤተሰቦቿ ከመሄዷ አስቀድሞ በፃድቃኔ ማርያም ቤተክርስቲያን ፀበል በመከታተል ላይ እያለች በተከሰተ ድንገተኛ የመሬት መንሸራተት አደጋ ህይወቷ ማለፉ ተገለጠ። አደጋው የተከሰተው ሐምሌ 27 ቀን 2018 ዓ.ም ሲሆን፣ ተማሪዋ በአካባቢው በነበረችበት ወቅት ባጋጠመው የመሬት መንሸራተት ህይወቷን ልታጣ ችላለች።
ተማሪ ሀብታሟ በቀለ በትምህርት ገበታዋ ካስመዘገበችው የላቀ ውጤት ባሻገር በመልካም ስነ-ምግባሯ፣ በታታሪነቷ እና በተግባቢነቷ በዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ ዘንድ ከፍተኛ ተወዳጅነት የነበራት ተማሪ ነበረች። በተለይም በምስለ ችሎት ውድድሮች በምታሳየው የላቀ የህግ ችሎታ እንዲሁም ዩኒቨርሲቲው ለአካባቢው ማህበረሰብ በሚሰጠው የነፃ ህግ እርዳታ አገልግሎት ላይ በንቃት በመሳተፍ የጎላ አስተዋጽኦ ስታበረክት እንደነበር ተገልጻለች።
የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ማኔጅመንት በተማሪ ሀብታሟ ድንገተኛ ህልፈት የተሰማውን ጥልቅ ሐዘን ገልጾ፣ ለቤተሰቦቿ፣ ለወዳጅ ዘመዶቿ እና ለመላው የዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ መፅናናትን ተመኝቷል።
#fastmereja I በድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ የ4ኛ ዓመት የህግ ትምህርት ተማሪ የሆነችው ሀብታሟ በቀለ ለእረፍት ወደ ቤተሰቦቿ ከመሄዷ አስቀድሞ በፃድቃኔ ማርያም ቤተክርስቲያን ፀበል በመከታተል ላይ እያለች በተከሰተ ድንገተኛ የመሬት መንሸራተት አደጋ ህይወቷ ማለፉ ተገለጠ። አደጋው የተከሰተው ሐምሌ 27 ቀን 2018 ዓ.ም ሲሆን፣ ተማሪዋ በአካባቢው በነበረችበት ወቅት ባጋጠመው የመሬት መንሸራተት ህይወቷን ልታጣ ችላለች።
ተማሪ ሀብታሟ በቀለ በትምህርት ገበታዋ ካስመዘገበችው የላቀ ውጤት ባሻገር በመልካም ስነ-ምግባሯ፣ በታታሪነቷ እና በተግባቢነቷ በዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ ዘንድ ከፍተኛ ተወዳጅነት የነበራት ተማሪ ነበረች። በተለይም በምስለ ችሎት ውድድሮች በምታሳየው የላቀ የህግ ችሎታ እንዲሁም ዩኒቨርሲቲው ለአካባቢው ማህበረሰብ በሚሰጠው የነፃ ህግ እርዳታ አገልግሎት ላይ በንቃት በመሳተፍ የጎላ አስተዋጽኦ ስታበረክት እንደነበር ተገልጻለች።
የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ማኔጅመንት በተማሪ ሀብታሟ ድንገተኛ ህልፈት የተሰማውን ጥልቅ ሐዘን ገልጾ፣ ለቤተሰቦቿ፣ ለወዳጅ ዘመዶቿ እና ለመላው የዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ መፅናናትን ተመኝቷል።
2 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ የኢትዮጵያ ህዝባዊ አብዮታዊ ፓርቲ (ኢህአፓ) የህዝብ ግንኙነት ኃላፊን ጨምሮ ከፓርቲው ጋር ግንኙነት ያላቸውን ሶስት ግለሰቦች ህገ-መንግስታዊ ስርአቱን በኃይል ለመናድ አሴረዋል በሚል ወንጀል ከሷቸዋል። ፖሊስ በነዚህ ግለሰቦች ላይ ተጨማሪ ምርመራ ለማድረግ የ14 ቀናት የጊዜ ቀጠሮ ጠይቋል።
ክሱ የቀረበው የፌደራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ቢሮ ለፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ አንደኛ ደረጃ የጊዜ ቀጠሮ ችሎት ባቀረበው የቅድመ ምርመራ ጥያቄ ላይ ነው። ይህ የሆነው ኢህአፓ የሶስቱን ግለሰቦች መታሰር ካረጋገጠ ከአንድ ቀን በኋላ ነው። የታሰሩት ግለሰቦች የፓርቲው የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ ይስሃቅ ወልዳይ፣ ከፓርቲው ጋር ግንኙነት ያላቸውን ግለሰቦች በህግ ሲወክሉ የነበሩት ጠበቃ አበራ ንጉስ አየነው፣ እና መምህር እንዲሁም የኢህአፓ አባል የሆነው አበበ አካሉ ክብረት ናቸው።
የኢህአፓ ዋና ፀሀፊ ሚስጥረ-ስላሴ ታምራት እስሩ መጀመሩን አረጋግጠው፣ ጠበቃ አበራ ንጉስ እና ይስሃቅ ወልዳይ መጀመሪያ በቁጥጥር ስር ሲውሉ፣ አበበ አካሉ ደግሞ በማግስቱ መታሰሩን ገልፀዋል። ፓርቲው ባወጣው አጭር መግለጫ፣ ግለሰቦቹ በሰላማዊ መንገድ ሀሳብን በነፃነት በመግለፃቸው ብቻ መታሰራቸውን አውግዞ፣ ሰላማዊ የፖለቲካ ትግል ወንጀል ስላልሆነ በአስቸኳይ እንዲፈቱ ጠይቋል።
በሌላ በኩል የፌደራል ፖሊስ የክስ መዝገብ እንደሚያትተው፣ ግለሰቦቹ የታሰሩት በፖለቲካዊ እንቅስቃሴ ሳይሆን በኃይል ስልጣን ለመያዝ በተቀናጀ ሴራ ውስጥ በመሳተፋቸው ነው። የፖሊስ የምርመራ ቢሮ እንዳለው፣ ተጠርጣሪዎቹ ህጋዊውን የፖለቲካ ፓርቲ እንደ ሽፋን በመጠቀም ከፓርቲው ህገ-ደንብ እና አላማ ውጪ መንግስትን በኃይል ለመገልበጥ ተንቀሳቅሰዋል። ፖሊስ አክሎም ግለሰቦቹ "የሀገር ውስጥ እና የውጭ ታሪካዊ ጠላቶች" ከተባሉት ህወሓት፣ ፅምዶ ከተባለ ቡድን እና ሌሎች ፀረ-ሰላም ኃይሎች ጋር በቅንጅት ሲሰሩ እንደነበር ወንጅሏል። በአዲስ አበባ አባላትን በመመልመል፣ የፀጥታ ኃይሎችን እንቅስቃሴ በመከታተል እና መረጃዎችን ለታጠቁ ኃይሎች በማስተላለፍ ተሳትፈዋል ተብለዋል።
ፖሊስ በክሱ ላይ እንዳሰፈረው ተጠርጣሪዎቹ የፖለቲካ፣ የወታደራዊ ስልጠና፣ የሚዲያ ፕሮፓጋንዳ እና የድርጊት መርሃ-ግብር አስፈፃሚ ክንፎችን በማዋቀር ህገ-ወጥ አደረጃጀት ፈጥረዋል። አንከር ሚዲያ፣ ኢትዮ-ፎረም እና ኢትዮ 360 ሚዲያን ጨምሮ በውጭ ከሚገኙ መገናኛ ብዙሃን ጋር በመተባበር ህዝቡን በመንግስት ላይ ለማነሳሳት የሀሰት መረጃዎችን ሲያሰራጩ እንደነበርም ተጠቅሷል።
ከዚህም ባሻገር ከከፍተኛ የህወሓት አመራሮች ጋር በሚስጥር በመገናኘት በአዲስ አበባ በሚገኙ የመንግስት የፀጥታ ተቋማት እና ከፍተኛ ባለስልጣናት ላይ የሽብር ጥቃት ለማድረስ ዝግጅት ሲያደርጉ በፀጥታ ኃይሎች ጥብቅ ክትትል በቁጥጥር ስር መዋላቸው ተገልጿል። ጉዳዩ እጅግ ውስብስብ እና ሀገራዊ አንድነትን የሚያፈርስ መሆኑን የገለፀው ፖሊስ፣ ተጠርጣሪዎቹ በዋስ ቢለቀቁ ምስክሮችን ሊያባብሉ ወይም ሊያስፈራሩ ይችላሉ በሚል ተጨማሪ የ14 ቀን የምርመራ ጊዜ እንዲሰጠው ፍርድ ቤቱን ጠይቋል።
ክሱ የቀረበው የፌደራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ቢሮ ለፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ አንደኛ ደረጃ የጊዜ ቀጠሮ ችሎት ባቀረበው የቅድመ ምርመራ ጥያቄ ላይ ነው። ይህ የሆነው ኢህአፓ የሶስቱን ግለሰቦች መታሰር ካረጋገጠ ከአንድ ቀን በኋላ ነው። የታሰሩት ግለሰቦች የፓርቲው የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ ይስሃቅ ወልዳይ፣ ከፓርቲው ጋር ግንኙነት ያላቸውን ግለሰቦች በህግ ሲወክሉ የነበሩት ጠበቃ አበራ ንጉስ አየነው፣ እና መምህር እንዲሁም የኢህአፓ አባል የሆነው አበበ አካሉ ክብረት ናቸው።
የኢህአፓ ዋና ፀሀፊ ሚስጥረ-ስላሴ ታምራት እስሩ መጀመሩን አረጋግጠው፣ ጠበቃ አበራ ንጉስ እና ይስሃቅ ወልዳይ መጀመሪያ በቁጥጥር ስር ሲውሉ፣ አበበ አካሉ ደግሞ በማግስቱ መታሰሩን ገልፀዋል። ፓርቲው ባወጣው አጭር መግለጫ፣ ግለሰቦቹ በሰላማዊ መንገድ ሀሳብን በነፃነት በመግለፃቸው ብቻ መታሰራቸውን አውግዞ፣ ሰላማዊ የፖለቲካ ትግል ወንጀል ስላልሆነ በአስቸኳይ እንዲፈቱ ጠይቋል።
በሌላ በኩል የፌደራል ፖሊስ የክስ መዝገብ እንደሚያትተው፣ ግለሰቦቹ የታሰሩት በፖለቲካዊ እንቅስቃሴ ሳይሆን በኃይል ስልጣን ለመያዝ በተቀናጀ ሴራ ውስጥ በመሳተፋቸው ነው። የፖሊስ የምርመራ ቢሮ እንዳለው፣ ተጠርጣሪዎቹ ህጋዊውን የፖለቲካ ፓርቲ እንደ ሽፋን በመጠቀም ከፓርቲው ህገ-ደንብ እና አላማ ውጪ መንግስትን በኃይል ለመገልበጥ ተንቀሳቅሰዋል። ፖሊስ አክሎም ግለሰቦቹ "የሀገር ውስጥ እና የውጭ ታሪካዊ ጠላቶች" ከተባሉት ህወሓት፣ ፅምዶ ከተባለ ቡድን እና ሌሎች ፀረ-ሰላም ኃይሎች ጋር በቅንጅት ሲሰሩ እንደነበር ወንጅሏል። በአዲስ አበባ አባላትን በመመልመል፣ የፀጥታ ኃይሎችን እንቅስቃሴ በመከታተል እና መረጃዎችን ለታጠቁ ኃይሎች በማስተላለፍ ተሳትፈዋል ተብለዋል።
ፖሊስ በክሱ ላይ እንዳሰፈረው ተጠርጣሪዎቹ የፖለቲካ፣ የወታደራዊ ስልጠና፣ የሚዲያ ፕሮፓጋንዳ እና የድርጊት መርሃ-ግብር አስፈፃሚ ክንፎችን በማዋቀር ህገ-ወጥ አደረጃጀት ፈጥረዋል። አንከር ሚዲያ፣ ኢትዮ-ፎረም እና ኢትዮ 360 ሚዲያን ጨምሮ በውጭ ከሚገኙ መገናኛ ብዙሃን ጋር በመተባበር ህዝቡን በመንግስት ላይ ለማነሳሳት የሀሰት መረጃዎችን ሲያሰራጩ እንደነበርም ተጠቅሷል።
ከዚህም ባሻገር ከከፍተኛ የህወሓት አመራሮች ጋር በሚስጥር በመገናኘት በአዲስ አበባ በሚገኙ የመንግስት የፀጥታ ተቋማት እና ከፍተኛ ባለስልጣናት ላይ የሽብር ጥቃት ለማድረስ ዝግጅት ሲያደርጉ በፀጥታ ኃይሎች ጥብቅ ክትትል በቁጥጥር ስር መዋላቸው ተገልጿል። ጉዳዩ እጅግ ውስብስብ እና ሀገራዊ አንድነትን የሚያፈርስ መሆኑን የገለፀው ፖሊስ፣ ተጠርጣሪዎቹ በዋስ ቢለቀቁ ምስክሮችን ሊያባብሉ ወይም ሊያስፈራሩ ይችላሉ በሚል ተጨማሪ የ14 ቀን የምርመራ ጊዜ እንዲሰጠው ፍርድ ቤቱን ጠይቋል።
2 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) ከትላንትናው እለት ጀምሮ 48 ዓይናለም ንጉሤ የሚመሩት የገቢዎች ሚኒስቴር እና የጉምሩክ ባለስልጣን ሰራተኞች በሙስና ወንጀል ተጠርጥረው በእስር ላይ እንደሚገኙ ታውቋል። ይህ እርምጃ መንግስት በተለያዩ ተቋማት ላይ እየወሰደ ያለው ተከታታይ የእስር ዘመቻ አካል ቢሆንም፣ የዘመቻው አካሄድ እና ኢላማ ግን በፖለቲከኞች ዘንድ ጠንካራ ትችት እያስተናገደ ይገኛል።
የአሁኑ የገቢዎች እና ጉምሩክ ሰራተኞች እስር፣ ከዚህ ቀደም በተለያዩ የመንግስት ሚኒስቴር መስሪያ ቤቶች ከተወሰዱ ተመሳሳይ የህግ እርምጃዎች ጋር ተዳምሮ የሚታይ ነው። ከዚህ እስር ቀደም ብሎ ሙፈሪያት ካሚል በምትመራው በስራና ክህሎት ሚኒስቴር ዜጎችን በህገ-ወጥ መንገድ ከሀገር በማስወጣት ወንጀል የተጠረጠሩ ሰራተኞች በሙስና መታሰራቸው ይታወሳል። በተመሳሳይ ከወራት በፊት ከነዳጅ አቅርቦት እና ስርጭት ጋር በተያያዘ በተፈጠረ የሙስና ወንጀል ካሳሁን ጎፌ የሜሩት የንግድ ሚኒስቴር ሰራተኞች በቁጥጥር ስር የዋሉ ሲሆን፣ አርሶ አደሩን በከፍተኛ ሁኔታ ካማረረው የማዳበሪያ አቅርቦት መጓተት እና ሙስና ጋር በተያያዘም የባህር ትራንዚት ሰራተኞች ተይዘው እንደነበር አይዘነጋም።
እነዚህ ተከታታይ የፀረ-ሙስና እርምጃዎች በታችኛው እና መካከለኛው የሰራተኛ እርከን ላይ ያተኮሩ መሆናቸው የዘመቻውን ታማኝነት ጥያቄ ውስጥ ከቶታል። ፖለቲከኛ ጀዋር መሐመድ ይህንን ሁኔታ አስመልክቶ ባቀረበው ጠንካራ ትችት፣ እነዚህ ሁሉ ከሙስና ጋር የተያያዙ እስሮች አንድ ትልቅ ነገር እንደሚጎድላቸው አመላክቷል።
እንደ ጀዋር ትንታኔ ይህ መጠነ-ሰፊ እና የተደራጀ ሙስና በየተቋማቱ ሲፈፀም፣ የየመስሪያ ቤቶቹ ዋና ሀላፊ የሆኑት እና በሙስናው ውስጥ በቀጥታ ተሳታፊና ተጠቃሚ የሆኑት ሚኒስትሮች ምንም አይነት የህግ ተጠያቂነት አልተደረገባቸውም። የፍትህ ስርዓቱ ዋና ዋናዎቹን የሙስና ጠንሳሾች ከመንካት ይልቅ፣ ጫፍ ላይ ያሉትን ፈፃሚዎች ብቻ ማሰሩ "ሻርኮቹን ትቶ ትናንሽ አሳዎችን ማጥመድ" ነው ሲል የፀረ-ሙስና ዘመቻውን ይዘት አጣጥሎታል።
ይህ እይታ የሙስና ችግር ስር ሰደድ መሆኑን እና እውነተኛ መፍትሄ ለማምጣት ከታችኛው እርከን ባለፈ ስልጣን ላይ ያሉ የዋና ተቋም መሪዎችንም በህግ ፊት እኩል ተጠያቂ ማድረግ እንደሚያስፈልግ አጉልቶ የሚያሳይ ነው።
የአሁኑ የገቢዎች እና ጉምሩክ ሰራተኞች እስር፣ ከዚህ ቀደም በተለያዩ የመንግስት ሚኒስቴር መስሪያ ቤቶች ከተወሰዱ ተመሳሳይ የህግ እርምጃዎች ጋር ተዳምሮ የሚታይ ነው። ከዚህ እስር ቀደም ብሎ ሙፈሪያት ካሚል በምትመራው በስራና ክህሎት ሚኒስቴር ዜጎችን በህገ-ወጥ መንገድ ከሀገር በማስወጣት ወንጀል የተጠረጠሩ ሰራተኞች በሙስና መታሰራቸው ይታወሳል። በተመሳሳይ ከወራት በፊት ከነዳጅ አቅርቦት እና ስርጭት ጋር በተያያዘ በተፈጠረ የሙስና ወንጀል ካሳሁን ጎፌ የሜሩት የንግድ ሚኒስቴር ሰራተኞች በቁጥጥር ስር የዋሉ ሲሆን፣ አርሶ አደሩን በከፍተኛ ሁኔታ ካማረረው የማዳበሪያ አቅርቦት መጓተት እና ሙስና ጋር በተያያዘም የባህር ትራንዚት ሰራተኞች ተይዘው እንደነበር አይዘነጋም።
እነዚህ ተከታታይ የፀረ-ሙስና እርምጃዎች በታችኛው እና መካከለኛው የሰራተኛ እርከን ላይ ያተኮሩ መሆናቸው የዘመቻውን ታማኝነት ጥያቄ ውስጥ ከቶታል። ፖለቲከኛ ጀዋር መሐመድ ይህንን ሁኔታ አስመልክቶ ባቀረበው ጠንካራ ትችት፣ እነዚህ ሁሉ ከሙስና ጋር የተያያዙ እስሮች አንድ ትልቅ ነገር እንደሚጎድላቸው አመላክቷል።
እንደ ጀዋር ትንታኔ ይህ መጠነ-ሰፊ እና የተደራጀ ሙስና በየተቋማቱ ሲፈፀም፣ የየመስሪያ ቤቶቹ ዋና ሀላፊ የሆኑት እና በሙስናው ውስጥ በቀጥታ ተሳታፊና ተጠቃሚ የሆኑት ሚኒስትሮች ምንም አይነት የህግ ተጠያቂነት አልተደረገባቸውም። የፍትህ ስርዓቱ ዋና ዋናዎቹን የሙስና ጠንሳሾች ከመንካት ይልቅ፣ ጫፍ ላይ ያሉትን ፈፃሚዎች ብቻ ማሰሩ "ሻርኮቹን ትቶ ትናንሽ አሳዎችን ማጥመድ" ነው ሲል የፀረ-ሙስና ዘመቻውን ይዘት አጣጥሎታል።
ይህ እይታ የሙስና ችግር ስር ሰደድ መሆኑን እና እውነተኛ መፍትሄ ለማምጣት ከታችኛው እርከን ባለፈ ስልጣን ላይ ያሉ የዋና ተቋም መሪዎችንም በህግ ፊት እኩል ተጠያቂ ማድረግ እንደሚያስፈልግ አጉልቶ የሚያሳይ ነው።
2 days ago
በትግራይ በዘውዱ ሀፍቱ ግድያ እድሜ ልክ ተፈርዶባቸው የነበሩ ግለሰቦች ከእስር መፈታታቸውን 'ይኾኖ' ማህበር አስታወቀ
በትግራይ ክልል ወጣት ዘውዱ ሀፍቱን በመግደል ወንጀል በእድሜ ልክ እስራት ተፈርዶባቸው የነበሩት ያሬድ ገብረሥላሴ እና አንገሶም ኃይለማርያም ከእስር መፈታታቸውን በክልሉ የሚንቀሳቀሰው የሴቶች መብት ተሟጋች ድርጅት 'ይኾኖ' (Yikhono) አስታወቀ።
እንደ ማህበሩ ገለፃ፣ ሁለቱ ግለሰቦች በፈጸሙት ዘግናኝ የግድያ ወንጀል ጥፋተኛ ሆነው ተገኝተው የጽኑ እስራት ውሳኔ ከተላለፈባቸው ገና አንድ ወር ያህል እንኳ ሳይሞላው ነው ከእስር ነፃ የወጡት።
ዕድሜዋ 32 የነበረችው ዘውዱ ሀፍቱ፣ ነሐሴ 13 ቀን 2015 ዓ.ም አመሻሽ ላይ በታቀደ ጥቃት በህዝብ ፊት በደረሰባት ከፍተኛ ድብደባ እና በመኪና በመጨፈለቋ ህይወቷ ማለፉ ይታወሳል።
ጉዳዩ በፍርድ ቤት ሲታይ በቆየባቸው ሁለት ዓመታት ውስጥ፦
በዳኞች ላይ ይደርስ የነበረ ዛቻ እና በችሎት ውስጥ የተፈጠሩ ረብሻዎች ሂደቱን ሲያስተጓጉሉት መቆየታቸው ተገልጿል።
ፍርድ ቤቱ ጥፋተኝነታቸውን በማረጋገጥ ያለ ምንም ይቅርታ (ይግባኝ) የዕድሜ ልክ እስራት ውሳኔ አሳልፎ ነበር።
ከእስር ተፈተዋል የተባሉት ተከሳሾች ያሬድ ገብረሥላሴ እና አንገሶም ኃይለማርያም ሲሆኑ፣ ያሬድ በወቅቱ የትግራይ ፖሊስ ኮሚሽነር የነበሩት እና በአሁኑ ወቅት የ22ኛ ሰራዊት አዛዥ ሆነው የሚያገለግሉት የኮሚሽነር ገብረሥላሴ በላይ ልጅ እንደሆነ ተገልጿል።
የሴቶች መብት ተሟጋች ድርጅቶች እና ቤተሰቦች እንደሚያስረዱት፣ በምርመራው እና በፍትህ ሂደቱ ወቅት የባለስልጣናት ተፅዕኖ እና ጣልቃ ገብነት እንደነበር ጠቁመዋል።
የግለሰቦቹ ከእስር መፈታት በክልሉ የፍትህ ስርዓት እና በሕግ የበላይነት ላይ ትልቅ ጥያቄ ማስነሳቱን የጠቆመው 'ይቅኖ' ማህበር፣ ውሳኔው የሴቶችን ደህንነት አደጋ ላይ የሚጥል መሆኑን ገልጿል።
በአሁኑ ወቅት በማህበራዊ ሚዲያ #justiceforzewdu በሚሉ ሃሽታጎች ለወጣት ዘውዱ ሀፍቱ ፍትህ እንዲረጋገጥ፣ በፍትህ ስርዓቱ ላይ ጣልቃ በሚገቡ ባለስልጣናት ላይ ህጋዊ እርምጃ እንዲወሰድ እና የህግ የበላይነት እንዲከበር ጥሪዎች በመቅረብ ላይ ይገኛሉ።
Via ጉርሻ page
በትግራይ ክልል ወጣት ዘውዱ ሀፍቱን በመግደል ወንጀል በእድሜ ልክ እስራት ተፈርዶባቸው የነበሩት ያሬድ ገብረሥላሴ እና አንገሶም ኃይለማርያም ከእስር መፈታታቸውን በክልሉ የሚንቀሳቀሰው የሴቶች መብት ተሟጋች ድርጅት 'ይኾኖ' (Yikhono) አስታወቀ።
እንደ ማህበሩ ገለፃ፣ ሁለቱ ግለሰቦች በፈጸሙት ዘግናኝ የግድያ ወንጀል ጥፋተኛ ሆነው ተገኝተው የጽኑ እስራት ውሳኔ ከተላለፈባቸው ገና አንድ ወር ያህል እንኳ ሳይሞላው ነው ከእስር ነፃ የወጡት።
ዕድሜዋ 32 የነበረችው ዘውዱ ሀፍቱ፣ ነሐሴ 13 ቀን 2015 ዓ.ም አመሻሽ ላይ በታቀደ ጥቃት በህዝብ ፊት በደረሰባት ከፍተኛ ድብደባ እና በመኪና በመጨፈለቋ ህይወቷ ማለፉ ይታወሳል።
ጉዳዩ በፍርድ ቤት ሲታይ በቆየባቸው ሁለት ዓመታት ውስጥ፦
በዳኞች ላይ ይደርስ የነበረ ዛቻ እና በችሎት ውስጥ የተፈጠሩ ረብሻዎች ሂደቱን ሲያስተጓጉሉት መቆየታቸው ተገልጿል።
ፍርድ ቤቱ ጥፋተኝነታቸውን በማረጋገጥ ያለ ምንም ይቅርታ (ይግባኝ) የዕድሜ ልክ እስራት ውሳኔ አሳልፎ ነበር።
ከእስር ተፈተዋል የተባሉት ተከሳሾች ያሬድ ገብረሥላሴ እና አንገሶም ኃይለማርያም ሲሆኑ፣ ያሬድ በወቅቱ የትግራይ ፖሊስ ኮሚሽነር የነበሩት እና በአሁኑ ወቅት የ22ኛ ሰራዊት አዛዥ ሆነው የሚያገለግሉት የኮሚሽነር ገብረሥላሴ በላይ ልጅ እንደሆነ ተገልጿል።
የሴቶች መብት ተሟጋች ድርጅቶች እና ቤተሰቦች እንደሚያስረዱት፣ በምርመራው እና በፍትህ ሂደቱ ወቅት የባለስልጣናት ተፅዕኖ እና ጣልቃ ገብነት እንደነበር ጠቁመዋል።
የግለሰቦቹ ከእስር መፈታት በክልሉ የፍትህ ስርዓት እና በሕግ የበላይነት ላይ ትልቅ ጥያቄ ማስነሳቱን የጠቆመው 'ይቅኖ' ማህበር፣ ውሳኔው የሴቶችን ደህንነት አደጋ ላይ የሚጥል መሆኑን ገልጿል።
በአሁኑ ወቅት በማህበራዊ ሚዲያ #justiceforzewdu በሚሉ ሃሽታጎች ለወጣት ዘውዱ ሀፍቱ ፍትህ እንዲረጋገጥ፣ በፍትህ ስርዓቱ ላይ ጣልቃ በሚገቡ ባለስልጣናት ላይ ህጋዊ እርምጃ እንዲወሰድ እና የህግ የበላይነት እንዲከበር ጥሪዎች በመቅረብ ላይ ይገኛሉ።
Via ጉርሻ page
2 days ago
እስራኤል አሽከርካሪ አልባ የታክሲ አግልግሎት ልትጀምር ነው
#ethiopia | እስራኤል በራሳቸው የሚንቀሳቀሱ አሽከርካሪ አልባ ተሽከርካሪዎችን በ2027 አገልግሎቱን በይፋ ልታስጀምር ነው።
እስራኤል ይህንን አገልግሎት አስቀድማ ለማስጀመር ከባለፉት አምስት አመታት ጀምራ ጥረት ስታደርግ ነበር ሲል ዘ ጀሩሳሌም ፖስት የዘገበው።
የመንግስት መስሪያ ቤቶች የራሳቸውን የህግ ማዕቀፍ ለማዘጋጀት ባለፉት አምስት ዓመታት ጥረት ሲያደርጉ የቆዩ ቢሆንም ወጥ የሆነ ዓለም አቀፍ የቴክኖሎጂና የደህንነት ስታንዳርድ ባለመኖሩ ምክንያት ሂደቱ ሲጓተት ቆይቷል ነው የተባለው።
ነገር ግን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የተሽከርካሪዎች ህግ አውጪ አካል በቅርቡ ያጸደቀው አዲስ የደህንነትና የቁጥጥር መመሪያ አገልግሎቱ ለማስጀመር ረድቷል ተብሏል።
አዲሱ የሕግ ማዕቀፍ አሽከርካሪ አልባ ተሽከርካሪዎች ከሰው አሽከርካሪ ያላነሰ ወይም የተሻለ የደህንነት ብቃት ሊኖራቸው እንደሚገባ ያስገድዳል።
በዚህም መሰረት አዲሱ የአውሮፓ ስታንዳርድ እስራኤል ውስጥ በቀጥታ ተግባራዊ የሚሆን ይሆናል።
የእስራኤል የትራንስፖርት ሚኒስቴር ያለ አሽከርካሪ የሚሰሩ ዘመናዊ ተሽከርካሪዎችን ወደ ሀገር ውስጥ ለማስገባት ለአስመጪዎች ፍቃድ ለመስጠት የሚያስችለውን ዝግጅት እያፋጠነ ይገኛል ተብሏል።
ሔኖክ ወ/ገብርኤል
#ethiopia #getutemesgen #getunews #israel #taxi #transport #technology
#ethiopia | እስራኤል በራሳቸው የሚንቀሳቀሱ አሽከርካሪ አልባ ተሽከርካሪዎችን በ2027 አገልግሎቱን በይፋ ልታስጀምር ነው።
እስራኤል ይህንን አገልግሎት አስቀድማ ለማስጀመር ከባለፉት አምስት አመታት ጀምራ ጥረት ስታደርግ ነበር ሲል ዘ ጀሩሳሌም ፖስት የዘገበው።
የመንግስት መስሪያ ቤቶች የራሳቸውን የህግ ማዕቀፍ ለማዘጋጀት ባለፉት አምስት ዓመታት ጥረት ሲያደርጉ የቆዩ ቢሆንም ወጥ የሆነ ዓለም አቀፍ የቴክኖሎጂና የደህንነት ስታንዳርድ ባለመኖሩ ምክንያት ሂደቱ ሲጓተት ቆይቷል ነው የተባለው።
ነገር ግን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የተሽከርካሪዎች ህግ አውጪ አካል በቅርቡ ያጸደቀው አዲስ የደህንነትና የቁጥጥር መመሪያ አገልግሎቱ ለማስጀመር ረድቷል ተብሏል።
አዲሱ የሕግ ማዕቀፍ አሽከርካሪ አልባ ተሽከርካሪዎች ከሰው አሽከርካሪ ያላነሰ ወይም የተሻለ የደህንነት ብቃት ሊኖራቸው እንደሚገባ ያስገድዳል።
በዚህም መሰረት አዲሱ የአውሮፓ ስታንዳርድ እስራኤል ውስጥ በቀጥታ ተግባራዊ የሚሆን ይሆናል።
የእስራኤል የትራንስፖርት ሚኒስቴር ያለ አሽከርካሪ የሚሰሩ ዘመናዊ ተሽከርካሪዎችን ወደ ሀገር ውስጥ ለማስገባት ለአስመጪዎች ፍቃድ ለመስጠት የሚያስችለውን ዝግጅት እያፋጠነ ይገኛል ተብሏል።
ሔኖክ ወ/ገብርኤል
#ethiopia #getutemesgen #getunews #israel #taxi #transport #technology
Sponsored by
Surafel
2 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የትራምፕ አስተዳደር ባለፈው ዓመት በውጭ ሀገር የዩኒቨርሲቲ እና የኮሌጅ ተማሪዎች ላይ የጀመረውን ጥብቅ ቁጥጥር ተከትሎ፣ ለቻይና እና ህንድ አመልካቾች የሚሰጠው የተማሪነት ቪዛ መጠን በከፍተኛ ሁኔታ መቀነሱን አዲስ ጥናት አመላከተ። መቀመጫውን ዋሽንግተን ያደረገው ሴንተር ፎር ኢሚግሬሽን ስተዲስ የተሰኘው ተቋም እንዳወጣው መረጃ፣ ከግንቦት እስከ ነሐሴ ሁለት ሺህ ሃያ አምስት ባለው ጊዜ ውስጥ ለቻይናውያን ተማሪዎች የተሰጠው ቪዛ በሁለት ሺህ አስራ ሰባት ከነበረው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር በአርባ ስድስት በመቶ ቀንሷል። በህንድ ተማሪዎች ላይ ደግሞ የስልሳ በመቶ ቅናሽ ታይቷል።
ቻይናውያን እና ህንዳውያን ተማሪዎች በአሜሪካ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ውስጥ ከሚማሩት አጠቃላይ የውጭ ሀገር ተማሪዎች ሃምሳ ሶስት በመቶውን ይሸፍናሉ። የተቋሙ ከፍተኛ የህግ ተመራማሪ ጆርጅ ፊሽማን ባወጡት ትንታኔ፣ ይህ የቪዛ ቅናሽ ለትምህርት ወደ አሜሪካ የሚገቡትን የውጭ ዜጎች አጠቃላይ ቁጥር በከፍተኛ ደረጃ የሚጎዳ መሆኑን አስገንዝበዋል። ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በሁለተኛው የስልጣን ዘመናቸው የከፍተኛ ትምህርት ማሻሻያን ኢላማ በማድረግ የጀመሩት ጫና፣ ጉዳዩን ወደ ግላዊ ፍልሚያነት የቀየረው ይመስላል።
ከቅርብ ዓመታት ወዲህ የትምህርት ዘርፉ ከስደተኞች ጉዳይ እስከ የፆታ አመለካከት፣ እንዲሁም ከተማሪዎች የብድር ስረዛ እስከ ካምፓስ ውስጥ የመናገር ነፃነት ድረስ የባህል እና የፖለቲካ ሽኩቻዎች ማዕከል ሆኗል። የሪፐብሊካን ፓርቲ አባላት በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ላይ የቆየ ጥርጣሬ ያላቸው ሲሆን፣ ምሁራን ወጣቶችን አክራሪ በሆኑ የፖለቲካ አመለካከቶች እየመረዙ ነው ብለው ይከሳሉ። ትራምፕም የኮሌጅ ካምፓሶች ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ በአክራሪነት ተወርረዋል በማለት ወቀሳ አቅርበዋል። የፕሬዝዳንቱ ዋነኛ ትኩረት የብዝሃነት፣ የእኩልነት እና የአካታችነት ፖሊሲዎችን በመቀልበስ፣ የተወሰኑ ተማሪዎች ያላግባብ ተጠቃሚ እየሆኑ ነው ያሉትን አሰራር ማስቆም ላይ ያነጣጠረ ነው።
ፕሬዝዳንት ትራምፕ የፌደራል መንግስቱን ስልጣን በመጠቀም የዩኒቨርሲቲዎችን የገንዘብ ድጋፍ ለማቋረጥ በማስፈራራት እና የውጭ ሀገር ተማሪዎችን መብት በመገደብ ላይ ይገኛሉ። ዩኒቨርሲቲዎች ተማሪዎችን በሚቀበሉበት መንገድ፣ በትምህርት ስርዓታቸው እና በአጠቃላይ አሰራራቸው ላይ ታይቶ የማያውቅ ጣልቃ ገብነት እያደረጉ ነው። በአብዛኛው የፀረ ሴማዊነት ክሶችን ወይም የህግ እና ስርአት መርሆችን በመጠቀም የከፍተኛ ትምህርት አስተዳዳሪዎች ላይ ጥብቅ ምርመራ እንዲካሄድ እያስገደዱ ይገኛሉ። አሜሪካ ውስጥ የፍትሃዊነት ተደራሽነትን ለማረጋገጥ የወጡ የሲቪል መብቶች ህጎችን በመጠቀም፣ በታሪክ ተጨቁነው የነበሩ የህብረተሰብ ክፍሎችን የሚጠብቁ አሰራሮችን ወደ ኋላ ለመመለስ እየሰሩ መሆኑ ተጠቁሟል።
ይህ የትራምፕ አስተዳደር ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጋር የገጠመው ፍልሚያ ወደ አጠቃላይ ጦርነት ያደገ ሲሆን፣ በተለይም የእሳቸውን ፍላጎት ለማስተናገድ ፈቃደኛ ባልሆኑ እንደ ታዋቂው ሃርቫርድ ዩኒቨርሲቲ ባሉ ተቋማት ላይ ያነጣጠረ ጠንካራ እርምጃ እየተወሰደ መሆኑ በዘገባው ተብራርቷል።
ቻይናውያን እና ህንዳውያን ተማሪዎች በአሜሪካ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ውስጥ ከሚማሩት አጠቃላይ የውጭ ሀገር ተማሪዎች ሃምሳ ሶስት በመቶውን ይሸፍናሉ። የተቋሙ ከፍተኛ የህግ ተመራማሪ ጆርጅ ፊሽማን ባወጡት ትንታኔ፣ ይህ የቪዛ ቅናሽ ለትምህርት ወደ አሜሪካ የሚገቡትን የውጭ ዜጎች አጠቃላይ ቁጥር በከፍተኛ ደረጃ የሚጎዳ መሆኑን አስገንዝበዋል። ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በሁለተኛው የስልጣን ዘመናቸው የከፍተኛ ትምህርት ማሻሻያን ኢላማ በማድረግ የጀመሩት ጫና፣ ጉዳዩን ወደ ግላዊ ፍልሚያነት የቀየረው ይመስላል።
ከቅርብ ዓመታት ወዲህ የትምህርት ዘርፉ ከስደተኞች ጉዳይ እስከ የፆታ አመለካከት፣ እንዲሁም ከተማሪዎች የብድር ስረዛ እስከ ካምፓስ ውስጥ የመናገር ነፃነት ድረስ የባህል እና የፖለቲካ ሽኩቻዎች ማዕከል ሆኗል። የሪፐብሊካን ፓርቲ አባላት በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ላይ የቆየ ጥርጣሬ ያላቸው ሲሆን፣ ምሁራን ወጣቶችን አክራሪ በሆኑ የፖለቲካ አመለካከቶች እየመረዙ ነው ብለው ይከሳሉ። ትራምፕም የኮሌጅ ካምፓሶች ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ በአክራሪነት ተወርረዋል በማለት ወቀሳ አቅርበዋል። የፕሬዝዳንቱ ዋነኛ ትኩረት የብዝሃነት፣ የእኩልነት እና የአካታችነት ፖሊሲዎችን በመቀልበስ፣ የተወሰኑ ተማሪዎች ያላግባብ ተጠቃሚ እየሆኑ ነው ያሉትን አሰራር ማስቆም ላይ ያነጣጠረ ነው።
ፕሬዝዳንት ትራምፕ የፌደራል መንግስቱን ስልጣን በመጠቀም የዩኒቨርሲቲዎችን የገንዘብ ድጋፍ ለማቋረጥ በማስፈራራት እና የውጭ ሀገር ተማሪዎችን መብት በመገደብ ላይ ይገኛሉ። ዩኒቨርሲቲዎች ተማሪዎችን በሚቀበሉበት መንገድ፣ በትምህርት ስርዓታቸው እና በአጠቃላይ አሰራራቸው ላይ ታይቶ የማያውቅ ጣልቃ ገብነት እያደረጉ ነው። በአብዛኛው የፀረ ሴማዊነት ክሶችን ወይም የህግ እና ስርአት መርሆችን በመጠቀም የከፍተኛ ትምህርት አስተዳዳሪዎች ላይ ጥብቅ ምርመራ እንዲካሄድ እያስገደዱ ይገኛሉ። አሜሪካ ውስጥ የፍትሃዊነት ተደራሽነትን ለማረጋገጥ የወጡ የሲቪል መብቶች ህጎችን በመጠቀም፣ በታሪክ ተጨቁነው የነበሩ የህብረተሰብ ክፍሎችን የሚጠብቁ አሰራሮችን ወደ ኋላ ለመመለስ እየሰሩ መሆኑ ተጠቁሟል።
ይህ የትራምፕ አስተዳደር ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጋር የገጠመው ፍልሚያ ወደ አጠቃላይ ጦርነት ያደገ ሲሆን፣ በተለይም የእሳቸውን ፍላጎት ለማስተናገድ ፈቃደኛ ባልሆኑ እንደ ታዋቂው ሃርቫርድ ዩኒቨርሲቲ ባሉ ተቋማት ላይ ያነጣጠረ ጠንካራ እርምጃ እየተወሰደ መሆኑ በዘገባው ተብራርቷል።
3 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) በፌንቴክ የኢንቨስትመንት ማጭበርበር ወንጀል ተጠርጥረው በዋስትና ላይ የሚገኙት እነ አርቲስት ሰራዊት ፍቅሬ ጉዳይ አሁን ወደ ሌላ አሳሳቢ ደረጃ ተሸጋግሯል! አርቲስቶቹ በእጃቸው ላይ ያለውን የፍርድ ቤት ሂደት ወደ ሚዲያ በማውጣታቸው ያልታሰበ አደጋ አንዣቦባቸዋል።
ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው ሚስጥራዊ ምንጮች ለዘ-ሐበሻ እንደጠቆሙት፣ አቃቤ ህግ ይህንን የሚዲያ ላይ ቃለ-ምልልስ ተከትሎ ነገ ረቡዕ (ሐምሌ 29 ቀን) በሚኖረው ችሎት "የተሰጣቸው የዋስትና መብት ይነሳልኝ" የሚል ከባድ አቤቱታ ያቀርባል ተብሎ እየተጠበቀ ነው። ይህ ማለት ጥያቄው ተቀባይነት ካገኘ አርቲስቶቹ ዳግም ወደ እስር ቤት ሊመለሱ ይችላሉ ማለት ነው።
ነገሩ በዚህ ብቻ አላበቃም፤ ቃለ-ምልልሱ ወደ አየር ከመውጣቱ አስቀድሞ፣ ተጠርጣሪዎቹ "በከፍተኛው ፍርድ ቤት የታገደብን የባንክ ሂሳብ ይለቀቅልን" የሚል ጥያቄ ለችሎቱ አቅርበው ነበር። ፍርድ ቤቱም ጥያቄውን ከተመለከተ በኋላ፣ አቃቤ ህግ በዚህ የገንዘብ መለቀቅ አቤቱታ ላይ የራሱን አስተያየት ይዞ ሐምሌ 29 ቀን ፍርድ ቤት እንዲቀርብ ትዕዛዝ ሰጥቷል።
አርቲስቶቹ የታገደባቸውን ገንዘብ አስለቅቀው በነጻነት መንቀሳቀሳቸውን ይቀጥላሉ? ወይስ የሚዲያ ላይ ቆይታቸው ዋጋ አስከፍሏቸው ዋስትናቸው ተነጥቆ ከባድ ኪሳራ ውስጥ ይገባሉ? ነገ ረቡዕ የሚሰጠው የፍርድ ቤት ውሳኔ የጉዳዩን የመጨረሻ እልባት የሚያሳይ ይሆናል!
ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው ሚስጥራዊ ምንጮች ለዘ-ሐበሻ እንደጠቆሙት፣ አቃቤ ህግ ይህንን የሚዲያ ላይ ቃለ-ምልልስ ተከትሎ ነገ ረቡዕ (ሐምሌ 29 ቀን) በሚኖረው ችሎት "የተሰጣቸው የዋስትና መብት ይነሳልኝ" የሚል ከባድ አቤቱታ ያቀርባል ተብሎ እየተጠበቀ ነው። ይህ ማለት ጥያቄው ተቀባይነት ካገኘ አርቲስቶቹ ዳግም ወደ እስር ቤት ሊመለሱ ይችላሉ ማለት ነው።
ነገሩ በዚህ ብቻ አላበቃም፤ ቃለ-ምልልሱ ወደ አየር ከመውጣቱ አስቀድሞ፣ ተጠርጣሪዎቹ "በከፍተኛው ፍርድ ቤት የታገደብን የባንክ ሂሳብ ይለቀቅልን" የሚል ጥያቄ ለችሎቱ አቅርበው ነበር። ፍርድ ቤቱም ጥያቄውን ከተመለከተ በኋላ፣ አቃቤ ህግ በዚህ የገንዘብ መለቀቅ አቤቱታ ላይ የራሱን አስተያየት ይዞ ሐምሌ 29 ቀን ፍርድ ቤት እንዲቀርብ ትዕዛዝ ሰጥቷል።
አርቲስቶቹ የታገደባቸውን ገንዘብ አስለቅቀው በነጻነት መንቀሳቀሳቸውን ይቀጥላሉ? ወይስ የሚዲያ ላይ ቆይታቸው ዋጋ አስከፍሏቸው ዋስትናቸው ተነጥቆ ከባድ ኪሳራ ውስጥ ይገባሉ? ነገ ረቡዕ የሚሰጠው የፍርድ ቤት ውሳኔ የጉዳዩን የመጨረሻ እልባት የሚያሳይ ይሆናል!
3 days ago
ብሩስ ዊሊስ ባለቤት የባለቤቷን ህመም (FTD) ለመከታተል የሚያስችል ህግ እንዲፀድቅ ግፊት አደረገች
የታዋቂው የፊልም ኮከብ ብሩስ ዊሊስ ባለቤት የሆነችው ኤማ ሄሚንግ ዊሊስ፣ ባለቤቷ የተጠቃበትን 'የፊት ለፊት የጭንቅላት ክፍል መጎዳት' (Frontotemporal Degeneration - FTD) የተሰኘውን የመርሳት ህመም የሚከታተል ህግ እንዲፀድቅ ሰኞ ዕለት በካሊፎርኒያ ካፒቶል ከሚገኙ ህግ አውጪዎች ጋር በመሆን ግፊት አድርጋለች።
በሴናተር ሮጀር ኒየሎ የተዘጋጀው እና ኤማ ሄሚንግ ዊሊስ ድጋፏን የሰጠችለት ይህ ረቂቅ ህግ፣ የካሊፎርኒያ የህዝብ ጤና መምሪያ ስለ FTD ህመም መረጃዎችን እንዲሰበስብ የሚያስገድድ ነው። መምሪያው በአሁኑ ወቅት የሃንቲንግተን፣ የፓርኪንሰንስ፣ የአልዛይመርስ እና የማልቲፕል ስክለሮሲስ በሽታዎችን መረጃዎች በመሰብሰብ ላይ ይገኛል። የህጉን ሂደት በተመለከተ፣ ረቂቅ ህጉ ሀምሌ 1 ቀን የህግ አውጪው ምክር ቤት የአንድ ወር የክረምት እረፍት ከመውጣቱ በፊት በምክር ቤቱ ተጠባባቂ መዝገብ ውስጥ ሰፍሮ ነበር። ምክር ቤቱ ሰኞ ዕለት ስራውን የጀመረ ሲሆን፣ ረቂቅ ህጎችን ለማጽደቅ የአንድ ወር ጊዜ ብቻ ቀርቶታል። ይህ የህግ ማዕቀፍ እስከ ጥር 1፣ 2032 ድረስ የሚራዘም ሲሆን፣ የህጉ ትንታኔ እንደሚያሳየው ለሰራተኞች እና ለኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ክፍያን ጨምሮ በዓመት 2.7 ሚሊዮን ዶላር በጀት ይጠይቃል።
ኤማ ሰኞ ዕለት በካፒቶል በሰጠችው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ እንዳብራራችው፣ FTDን በነርቭ መጎዳት በሽታዎች መዝገብ ውስጥ ማካተት የካሊፎርኒያ ታካሚዎችን መቁጠር ብቻ ሳይሆን፣ በካሊፎርኒያ የሚገኙ የባዮቴክ ተመራማሪዎች ህክምና እና ፈውስ ለማግኘት የሚፈልጉትን ጠቃሚ የመረጃ ቋት መገንባት ነው። ባለቤቷ ለመጀመሪያ ጊዜ በ2022 በበሽታው መያዙ እንደታወቀ የጠቀሰችው ኤማ፣ አሁን ላይ ህመሙን የሚያዘገይ ወይም የሚያቆም ህክምና እንደሌለ ብታምንም፣ የህመሙን መረጃዎች መሰብሰብ ግን ለምርምር ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳለው ተናግራለች። ታዋቂው ተዋናይ ስለሚገኝበት ሁኔታ ተጠይቃ ስትመልስም፣ በዚህ እጅግ ጨካኝ በሆነ በሽታ ውስጥ ሆኖ ማድረግ የሚችለውን ያህል በጥሩ ሁኔታ ላይ ይገኛል ብዬ አስባለሁ ስትል ገልጻለች።
'ፒክስ ዲዚዝ' በመባልም የሚታወቀው ይህ ህመም፣ ከግንባር ጀርባ ወይም ከጆሮ አካባቢ ባሉ የጭንቅላት ክፍሎች ላይ በሚከሰት የነርቭ ሴሎች መጎዳት የሚመጣ የጭንቅላት እክል ነው። የበሽታው ምልክቶች የባህሪ እና የስብዕና ለውጥን፣ ስሜት አልባ መሆንን ፣ ውሳኔ የመስጠት፣ የመንቀሳቀስ እና የመናገር ችግርን፣ እንዲሁም ቃላትን የመረዳት አቅም ማጣትን ያካትታሉ።
የኤፍ ቲ ዲ ማህበር የጥብቅና እና የበጎ ፈቃደኞች ተሳትፎ ዳይሬክተር የሆኑት ሜጋን ቡዝቢ እንደገለጹት፣ የታካሚ ቤተሰቦች እነዚህ ምልክቶች ሲታዩ ከሐኪሞች ግልጽ የሆነ ምላሽ ለማግኘት ብዙ ጊዜ ይቸገራሉ። ዳይሬክተሯ አክለውም፣ ይህ ሁኔታ ለብዙ የካሊፎርኒያ ቤተሰቦች የFTD ምርመራ ውጤትን ለማግኘት የሚያደርጉት ረጅም እና አድካሚ ጉዞ እውነታ መሆኑን አብራርተዋል። በአሁኑ ወቅት በሽታውን ለማከም የሚረዱ ህክምናዎች እጅግ ውስን ሲሆኑ፣ ፈውስም እስካሁን አልተገኘለትም።
የታዋቂው የፊልም ኮከብ ብሩስ ዊሊስ ባለቤት የሆነችው ኤማ ሄሚንግ ዊሊስ፣ ባለቤቷ የተጠቃበትን 'የፊት ለፊት የጭንቅላት ክፍል መጎዳት' (Frontotemporal Degeneration - FTD) የተሰኘውን የመርሳት ህመም የሚከታተል ህግ እንዲፀድቅ ሰኞ ዕለት በካሊፎርኒያ ካፒቶል ከሚገኙ ህግ አውጪዎች ጋር በመሆን ግፊት አድርጋለች።
በሴናተር ሮጀር ኒየሎ የተዘጋጀው እና ኤማ ሄሚንግ ዊሊስ ድጋፏን የሰጠችለት ይህ ረቂቅ ህግ፣ የካሊፎርኒያ የህዝብ ጤና መምሪያ ስለ FTD ህመም መረጃዎችን እንዲሰበስብ የሚያስገድድ ነው። መምሪያው በአሁኑ ወቅት የሃንቲንግተን፣ የፓርኪንሰንስ፣ የአልዛይመርስ እና የማልቲፕል ስክለሮሲስ በሽታዎችን መረጃዎች በመሰብሰብ ላይ ይገኛል። የህጉን ሂደት በተመለከተ፣ ረቂቅ ህጉ ሀምሌ 1 ቀን የህግ አውጪው ምክር ቤት የአንድ ወር የክረምት እረፍት ከመውጣቱ በፊት በምክር ቤቱ ተጠባባቂ መዝገብ ውስጥ ሰፍሮ ነበር። ምክር ቤቱ ሰኞ ዕለት ስራውን የጀመረ ሲሆን፣ ረቂቅ ህጎችን ለማጽደቅ የአንድ ወር ጊዜ ብቻ ቀርቶታል። ይህ የህግ ማዕቀፍ እስከ ጥር 1፣ 2032 ድረስ የሚራዘም ሲሆን፣ የህጉ ትንታኔ እንደሚያሳየው ለሰራተኞች እና ለኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ክፍያን ጨምሮ በዓመት 2.7 ሚሊዮን ዶላር በጀት ይጠይቃል።
ኤማ ሰኞ ዕለት በካፒቶል በሰጠችው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ እንዳብራራችው፣ FTDን በነርቭ መጎዳት በሽታዎች መዝገብ ውስጥ ማካተት የካሊፎርኒያ ታካሚዎችን መቁጠር ብቻ ሳይሆን፣ በካሊፎርኒያ የሚገኙ የባዮቴክ ተመራማሪዎች ህክምና እና ፈውስ ለማግኘት የሚፈልጉትን ጠቃሚ የመረጃ ቋት መገንባት ነው። ባለቤቷ ለመጀመሪያ ጊዜ በ2022 በበሽታው መያዙ እንደታወቀ የጠቀሰችው ኤማ፣ አሁን ላይ ህመሙን የሚያዘገይ ወይም የሚያቆም ህክምና እንደሌለ ብታምንም፣ የህመሙን መረጃዎች መሰብሰብ ግን ለምርምር ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳለው ተናግራለች። ታዋቂው ተዋናይ ስለሚገኝበት ሁኔታ ተጠይቃ ስትመልስም፣ በዚህ እጅግ ጨካኝ በሆነ በሽታ ውስጥ ሆኖ ማድረግ የሚችለውን ያህል በጥሩ ሁኔታ ላይ ይገኛል ብዬ አስባለሁ ስትል ገልጻለች።
'ፒክስ ዲዚዝ' በመባልም የሚታወቀው ይህ ህመም፣ ከግንባር ጀርባ ወይም ከጆሮ አካባቢ ባሉ የጭንቅላት ክፍሎች ላይ በሚከሰት የነርቭ ሴሎች መጎዳት የሚመጣ የጭንቅላት እክል ነው። የበሽታው ምልክቶች የባህሪ እና የስብዕና ለውጥን፣ ስሜት አልባ መሆንን ፣ ውሳኔ የመስጠት፣ የመንቀሳቀስ እና የመናገር ችግርን፣ እንዲሁም ቃላትን የመረዳት አቅም ማጣትን ያካትታሉ።
የኤፍ ቲ ዲ ማህበር የጥብቅና እና የበጎ ፈቃደኞች ተሳትፎ ዳይሬክተር የሆኑት ሜጋን ቡዝቢ እንደገለጹት፣ የታካሚ ቤተሰቦች እነዚህ ምልክቶች ሲታዩ ከሐኪሞች ግልጽ የሆነ ምላሽ ለማግኘት ብዙ ጊዜ ይቸገራሉ። ዳይሬክተሯ አክለውም፣ ይህ ሁኔታ ለብዙ የካሊፎርኒያ ቤተሰቦች የFTD ምርመራ ውጤትን ለማግኘት የሚያደርጉት ረጅም እና አድካሚ ጉዞ እውነታ መሆኑን አብራርተዋል። በአሁኑ ወቅት በሽታውን ለማከም የሚረዱ ህክምናዎች እጅግ ውስን ሲሆኑ፣ ፈውስም እስካሁን አልተገኘለትም።
3 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የትራምፕ አስተዳደር ከ10 እስከ 12.5 በመቶ የሚደርስ ዓለም አቀፍ ታሪፍ (ቀረጥ) ለመጣል ያደረገውን አዲስ ሙከራ ለማገድ፣ 25 የአሜሪካ ግዛቶች ሰኞ ዕለት በአሜሪካ ዓለም አቀፍ የንግድ ፍርድ ቤት ክስ መስርተዋል።
ግዛቶቹ በክሳቸው እንዳስገነዘቡት፣ የአሜሪካ የንግድ ተወካይ ጽሕፈት ቤት በዓለም አቀፍ ደረጃ "የግዳጅ ስራን" ለመከላከል በሚል ያካሄደው ምርመራ ህገ-ወጥ የንግድ እገዳዎችን በድጋሚ ለመጣል የተቀነባበረ ሽፋን ነው። በተለምዶ ከአንድ ዓመት በላይ የሚወስደውን ምርመራ በ60 ሀገራት (ኢኮኖሚዎች) ላይ በሁለት ወር ተኩል ጊዜ ውስጥ ብቻ በችኮላ በማጠናቀቅ፣ አስተዳደሩ ቀድሞ የተወሰነ ውሳኔ ላይ መድረሱን እና እርምጃውም "የዘፈቀደ እና ህግን የጣሰ" መሆኑን ከሳሾቹ በጽኑ ተችተዋል። የኒውዮርክ አቃቤ ህግ ሌቲሻ ጄምስ ፕሬዝዳንቱ በፈለጋቸው ሀገራት ላይ ሰፊ ታሪፍ የመጣል ስልጣን እንደሌላቸው ሲያሰምሩበት፣ የክልሉ ገዥ ካቲ ሆቹል ደግሞ እርምጃውን የዕለት ተዕለት የሸቀጦች ዋጋን የሚያንር "በሰራተኛው ቤተሰብ ላይ የተጣለ ግብር" ሲሉ ኮንነውታል።
ግዛቶቹ የስራ አስፈፃሚው አካል ከኮንግረስ የታክስ ስልጣንን በህገ-ወጥ መንገድ ለመንጠቅ እየሞከረ መሆኑን በመግለጽ ፍርድ ቤቱ ታሪፉን ህገ-ወጥ ብሎ እንዲያግደው የጠየቁ ቢሆንም፣ ኋይት ሀውስ ግን ክሱን ውድቅ አድርጎታል። አስተዳደሩ የውጭ ሀገራት የሰራተኛ መብቶችን ባለማክበራቸው በአሜሪካ የንግድ እንቅስቃሴ እና ሰራተኞች ላይ የሚያደርሱትን ጫና ለመከላከል በህጋዊ መብቱ እና ስልጣኑ እየተጠቀመ መሆኑን የኋይት ሀውስ ቃል አቀባይ ኩሽ ዴሳይ ምላሽ ሰጥተዋል።
ግዛቶቹ በክሳቸው እንዳስገነዘቡት፣ የአሜሪካ የንግድ ተወካይ ጽሕፈት ቤት በዓለም አቀፍ ደረጃ "የግዳጅ ስራን" ለመከላከል በሚል ያካሄደው ምርመራ ህገ-ወጥ የንግድ እገዳዎችን በድጋሚ ለመጣል የተቀነባበረ ሽፋን ነው። በተለምዶ ከአንድ ዓመት በላይ የሚወስደውን ምርመራ በ60 ሀገራት (ኢኮኖሚዎች) ላይ በሁለት ወር ተኩል ጊዜ ውስጥ ብቻ በችኮላ በማጠናቀቅ፣ አስተዳደሩ ቀድሞ የተወሰነ ውሳኔ ላይ መድረሱን እና እርምጃውም "የዘፈቀደ እና ህግን የጣሰ" መሆኑን ከሳሾቹ በጽኑ ተችተዋል። የኒውዮርክ አቃቤ ህግ ሌቲሻ ጄምስ ፕሬዝዳንቱ በፈለጋቸው ሀገራት ላይ ሰፊ ታሪፍ የመጣል ስልጣን እንደሌላቸው ሲያሰምሩበት፣ የክልሉ ገዥ ካቲ ሆቹል ደግሞ እርምጃውን የዕለት ተዕለት የሸቀጦች ዋጋን የሚያንር "በሰራተኛው ቤተሰብ ላይ የተጣለ ግብር" ሲሉ ኮንነውታል።
ግዛቶቹ የስራ አስፈፃሚው አካል ከኮንግረስ የታክስ ስልጣንን በህገ-ወጥ መንገድ ለመንጠቅ እየሞከረ መሆኑን በመግለጽ ፍርድ ቤቱ ታሪፉን ህገ-ወጥ ብሎ እንዲያግደው የጠየቁ ቢሆንም፣ ኋይት ሀውስ ግን ክሱን ውድቅ አድርጎታል። አስተዳደሩ የውጭ ሀገራት የሰራተኛ መብቶችን ባለማክበራቸው በአሜሪካ የንግድ እንቅስቃሴ እና ሰራተኞች ላይ የሚያደርሱትን ጫና ለመከላከል በህጋዊ መብቱ እና ስልጣኑ እየተጠቀመ መሆኑን የኋይት ሀውስ ቃል አቀባይ ኩሽ ዴሳይ ምላሽ ሰጥተዋል።
3 days ago
(ዘ-ሐበሻ ሕይወት)) አደጋው ከተፈጸመ እነሆ አንድ ወር አልፎታል። የ50 ዓመቷን ኢትዮጵያዊት ሰርክአዲስ አበበ በቀለን ህይወት በከፍተኛ ስካር አሽከርክራ የቀጠፈችው የ28 ዓመቷ ማሪ ባህንድዋ፣ አሁን ላይ እስከ 20 ዓመታት ሊደርስ የሚችል የጽኑ እሥራት ፍርድ ከፊቷ ተደቅኗል። በጆርጂያ ግዛት ህግ መሰረት፣ አንደኛ ደረጃ የተሽከርካሪ ግድያ ብቻውን ከ3 እስከ 15 ዓመት የሚያስቀጣ ሲሆን፣ ከዚህ ጋር የተደራረቡት ሁለት የDUI (በስካር ማሽከርከር) እና የቸልተኝነት ወንጀሎች ሲታከሉበት፣ ማሪ የወጣትነት ዘመኗን ሙሉ በጨለማ የብረት አጥር ውስጥ እንድታሳልፍ ሊያደርጋት ይችላል።
ነገሩን ይበልጥ አሳዛኝ እና ልብ ሰባሪ የሚያደርገው ከግድያው ጀርባ ያለው የአደጋው መነሻ ምክንያት ነው። ማሪ የዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ብሔራዊ ቡድን የነፍስ ደጋፊ ነበረች። አደጋው ከመከሰቱ አንድ ቀን ቀደም ብሎ በአትላንታ ከተማ የተካሄደውን የኮንጎ የዓለም ዋንጫ ጨዋታ ስትከታተል እና በከፍተኛ ስሜት ስታከብር ውላለች። በዚያች ሌሊት በከፍተኛ ስካር ውስጥ ሆና ስታሽከረክረው የነበረው ጂፕ (Jeep Wrangler) መኪናዋ ላይም፣ የኮንጎ ደጋፊ መሆኗን የሚገልጹ ጽሁፎች እና መፈክሮች ተለጥፈውበት ነበር።
የኮንጎን እግር ኳስ ጨዋታ ድምቀት በከፍተኛ የአልኮል ስካር ታጅባ ስታከብር ያመሸችው ማሪ፣ የራሷን የደስታ ምሽት በንጹህ እግረኛ ደም አጥቅራዋለች። በዚያች የጭለማ ሌሊት ኮርትላንድ አቬኑ ላይ መንገዱን በሰላም እያቋረጠች የነበረችው ምስኪን ኢትዮጵያዊት፣ በመኪናዋ ላይ የኮንጎን መፈክር በለጠፈች እና ራሷን መቆጣጠር ባቃታት ሰካራም አሽከርካሪ የህይወት ጉዞዋ በድንገት እና በአሰቃቂ ሁኔታ ተቋጭቷል።
የአንዲት ሀላፊነት የጎደላት ግለሰብ የደስታ ስካር፣ የአንድን ኢትዮጵያዊት ቤተሰብ ለዘለዓለማዊ የሀዘን ማቅ አልብሷል። አሁን ፍርድ ቤቱ ማሪን ከህብረተሰቡ በማግለል ተመጣጣኝ የሆነውን የጽኑ እሥራት ቅጣት ያስተላልፋል ተብሎ በጉጉት የሚጠበቅ ሲሆን፣ ይህ አሳዛኝ ክስተት ግን በስካር የሚመጣ የሰከንድ ስህተት የሁለትን ሰዎች (የገዳይን እና የሟችን) ህይወት እንዴት ለዘለዓለም በጨለማ እንደሚያጠፋው ቁልጭ አድርጎ ያሳየ መሪር ትምህርት ሆኖ አልፏል።
ነገሩን ይበልጥ አሳዛኝ እና ልብ ሰባሪ የሚያደርገው ከግድያው ጀርባ ያለው የአደጋው መነሻ ምክንያት ነው። ማሪ የዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ብሔራዊ ቡድን የነፍስ ደጋፊ ነበረች። አደጋው ከመከሰቱ አንድ ቀን ቀደም ብሎ በአትላንታ ከተማ የተካሄደውን የኮንጎ የዓለም ዋንጫ ጨዋታ ስትከታተል እና በከፍተኛ ስሜት ስታከብር ውላለች። በዚያች ሌሊት በከፍተኛ ስካር ውስጥ ሆና ስታሽከረክረው የነበረው ጂፕ (Jeep Wrangler) መኪናዋ ላይም፣ የኮንጎ ደጋፊ መሆኗን የሚገልጹ ጽሁፎች እና መፈክሮች ተለጥፈውበት ነበር።
የኮንጎን እግር ኳስ ጨዋታ ድምቀት በከፍተኛ የአልኮል ስካር ታጅባ ስታከብር ያመሸችው ማሪ፣ የራሷን የደስታ ምሽት በንጹህ እግረኛ ደም አጥቅራዋለች። በዚያች የጭለማ ሌሊት ኮርትላንድ አቬኑ ላይ መንገዱን በሰላም እያቋረጠች የነበረችው ምስኪን ኢትዮጵያዊት፣ በመኪናዋ ላይ የኮንጎን መፈክር በለጠፈች እና ራሷን መቆጣጠር ባቃታት ሰካራም አሽከርካሪ የህይወት ጉዞዋ በድንገት እና በአሰቃቂ ሁኔታ ተቋጭቷል።
የአንዲት ሀላፊነት የጎደላት ግለሰብ የደስታ ስካር፣ የአንድን ኢትዮጵያዊት ቤተሰብ ለዘለዓለማዊ የሀዘን ማቅ አልብሷል። አሁን ፍርድ ቤቱ ማሪን ከህብረተሰቡ በማግለል ተመጣጣኝ የሆነውን የጽኑ እሥራት ቅጣት ያስተላልፋል ተብሎ በጉጉት የሚጠበቅ ሲሆን፣ ይህ አሳዛኝ ክስተት ግን በስካር የሚመጣ የሰከንድ ስህተት የሁለትን ሰዎች (የገዳይን እና የሟችን) ህይወት እንዴት ለዘለዓለም በጨለማ እንደሚያጠፋው ቁልጭ አድርጎ ያሳየ መሪር ትምህርት ሆኖ አልፏል።
Sponsored by
Surafel
4 days ago
በአትላንታ ጆርጂያ፣ ጠጥታ እያሽከረከረች የኢትዮጵያዊቷን ሕይወት የቀጠፈችው የ28 ዓመት ሴት ምን እንደሚጠብቃት የህግ ባለሙያዎች ተናገሩ - ልብ ሰባሪው ክስተት #atlantanews #justiceforserkadis #dui #diaspora #ethiopiancommunity
4 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) በሰሜን ኢትዮጵያ ትግራይ ክልል ኦገስት 1 ቀን በትግራይ ኃይሎች እና በኢትዮጵያ ብሔራዊ መከላከያ ሠራዊት (ENDF) መካከል ዳግም ያመረቀዘውን ግጭት ተከትሎ፣ የክልሉ ነዋሪዎች ለአዲስ የሰብዓዊ መብት ጥሰት አደጋ መጋለጣቸውን አምነስቲ ኢንተርናሽናል አስታወቀ። የምስራቅ እና ደቡባዊ አፍሪካ የአምነስቲ ኢንተርናሽናል ቀጠናዊ ዳይሬክተር ቲጌሬ ቻጉታህ ባወጡት መግለጫ፣ ማህበረሰቡ ከዚህ ቀደም የተፈጸሙበትን አሰቃቂ በደሎች ያለ ምንም ፍትህ እና ተጠያቂነት እያስተናገደ ባለበት በአሁኑ ወቅት፣ አዲሱ የትጥቅ ግጭት ነዋሪዎቹን ወደ ከፋ አደጋ ውስጥ ጥሏቸዋል ብለዋል።
ቀጠናዊ ዳይሬክተሩ አክለውም ይህ በትግራይ ዳግም ያገረሸው ጦርነት በአማራ እና በኦሮሚያ ክልሎች ቀጥሎ ከሚገኘው እና ተቋማቸው ከባድ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶችን እየመዘገበበት ካለው የትጥቅ ግጭት ጋር ሲደመር፣ ሀገሪቱ አፋጣኝ የሆነ ቀጠናዊ እና ዓለም አቀፋዊ የሰብዓዊ መብት ምርመራ ዘዴዎችን ወደ ነበረበት መመለስ እንዳለባት አመላካች ነው ሲሉ አሳስበዋል። ከህዳር 2013 እስከ ህዳር 2015 ዓ.ም. በተካሄደው ጦርነት የጦር ወንጀል እና በሰብዓዊነት ላይ የሚፈጸሙ ወንጀሎች ሊባሉ የሚችሉ ከባድ ጥሰቶች መመዝገባቸውን ያስታወሰው ተቋሙ፣ የኢትዮጵያ መንግስት ታማኝ ምርመራ አለማድረግን እና የጥፋተኞችን የህግ ተጠያቂነት ማስፈን አለመቻልን እንደ መደበኛ አሰራር ሊቆጥረው አይገባም ሲል አስጠንቅቋል።
በመሆኑም አምነስቲ ኢንተርናሽናል የፌደራል እና የትግራይ ባለስልጣናት የሲቪሎችን ጥበቃ ጨምሮ ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት መስፈርቶችን እንዲያከብሩ ጥሪ አቅርቧል። ከዚህም ባሻገር ገለልተኛ የሰብዓዊ መብት ታዛቢዎች እና የሰብዓዊ እርዳታ አቅራቢዎች ያለምንም እንቅፋት በቦታው ተገኝተው ስራቸውን እንዲያከናውኑ ሊፈቀድላቸው እንደሚገባ ተማጽኗል። ዓለም አቀፉ ማህበረሰብም በአዲስ አበባ እና በመቀሌ ከሚገኙ ባለስልጣናት ጋር በአስቸኳይ በመነጋገር በግጭቱ ለተጎዱ የትግራይ አካባቢዎች የነጻ ሚዲያዎች እና የሰብዓዊ መብት ታዛቢዎች ተደራሽነት እንዲረጋገጥ ተቋሙ ወትውቷል።
በኢትዮጵያ ውስጥ ይደረግ የነበረው ቀጠናዊ እና ዓለም አቀፋዊ የሰብዓዊ መብት ክትትል የተቋረጠው፣ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብዓዊ መብት ባለሙያዎች ኮሚሽን (ICHREE) እና የአፍሪካ የሰብዓዊ እና ህዝቦች መብት ኮሚሽን አጣሪ ቡድን የስራ ጊዜ ማብቃቱን ተከትሎ መሆኑን መግለጫው አስታውሷል። ይህንንም ተከትሎ የኢትዮጵያ መንግስት ዓለም አቀፍ የተጠያቂነት ጥረቶችን ለመከላከል ሲጠቀምበት የነበረውን የሽግግር ፍትህ ሂደት እርግፍ አድርጎ ትቶታል ሲል መግለጫው ወቅሷል። በሌላ በኩል ባለፉት ሁለት ወራት ውስጥ የትግራይ ባለስልጣናት ነጻ ሚዲያዎችን ከማፈን፣ በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎችን በግዳጅ ወደ ጦርነት ከመመልመል እና የዜጎችን ከቦታ ቦታ የመንቀሳቀስ መብት ከመገደብ ጋር የተያያዙ አፋኝ እርምጃዎችን እየወሰዱ መሆኑን የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች መመዝገባቸውን አምነስቲ አጋልጧል።
ቀጠናዊ ዳይሬክተሩ አክለውም ይህ በትግራይ ዳግም ያገረሸው ጦርነት በአማራ እና በኦሮሚያ ክልሎች ቀጥሎ ከሚገኘው እና ተቋማቸው ከባድ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶችን እየመዘገበበት ካለው የትጥቅ ግጭት ጋር ሲደመር፣ ሀገሪቱ አፋጣኝ የሆነ ቀጠናዊ እና ዓለም አቀፋዊ የሰብዓዊ መብት ምርመራ ዘዴዎችን ወደ ነበረበት መመለስ እንዳለባት አመላካች ነው ሲሉ አሳስበዋል። ከህዳር 2013 እስከ ህዳር 2015 ዓ.ም. በተካሄደው ጦርነት የጦር ወንጀል እና በሰብዓዊነት ላይ የሚፈጸሙ ወንጀሎች ሊባሉ የሚችሉ ከባድ ጥሰቶች መመዝገባቸውን ያስታወሰው ተቋሙ፣ የኢትዮጵያ መንግስት ታማኝ ምርመራ አለማድረግን እና የጥፋተኞችን የህግ ተጠያቂነት ማስፈን አለመቻልን እንደ መደበኛ አሰራር ሊቆጥረው አይገባም ሲል አስጠንቅቋል።
በመሆኑም አምነስቲ ኢንተርናሽናል የፌደራል እና የትግራይ ባለስልጣናት የሲቪሎችን ጥበቃ ጨምሮ ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት መስፈርቶችን እንዲያከብሩ ጥሪ አቅርቧል። ከዚህም ባሻገር ገለልተኛ የሰብዓዊ መብት ታዛቢዎች እና የሰብዓዊ እርዳታ አቅራቢዎች ያለምንም እንቅፋት በቦታው ተገኝተው ስራቸውን እንዲያከናውኑ ሊፈቀድላቸው እንደሚገባ ተማጽኗል። ዓለም አቀፉ ማህበረሰብም በአዲስ አበባ እና በመቀሌ ከሚገኙ ባለስልጣናት ጋር በአስቸኳይ በመነጋገር በግጭቱ ለተጎዱ የትግራይ አካባቢዎች የነጻ ሚዲያዎች እና የሰብዓዊ መብት ታዛቢዎች ተደራሽነት እንዲረጋገጥ ተቋሙ ወትውቷል።
በኢትዮጵያ ውስጥ ይደረግ የነበረው ቀጠናዊ እና ዓለም አቀፋዊ የሰብዓዊ መብት ክትትል የተቋረጠው፣ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብዓዊ መብት ባለሙያዎች ኮሚሽን (ICHREE) እና የአፍሪካ የሰብዓዊ እና ህዝቦች መብት ኮሚሽን አጣሪ ቡድን የስራ ጊዜ ማብቃቱን ተከትሎ መሆኑን መግለጫው አስታውሷል። ይህንንም ተከትሎ የኢትዮጵያ መንግስት ዓለም አቀፍ የተጠያቂነት ጥረቶችን ለመከላከል ሲጠቀምበት የነበረውን የሽግግር ፍትህ ሂደት እርግፍ አድርጎ ትቶታል ሲል መግለጫው ወቅሷል። በሌላ በኩል ባለፉት ሁለት ወራት ውስጥ የትግራይ ባለስልጣናት ነጻ ሚዲያዎችን ከማፈን፣ በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎችን በግዳጅ ወደ ጦርነት ከመመልመል እና የዜጎችን ከቦታ ቦታ የመንቀሳቀስ መብት ከመገደብ ጋር የተያያዙ አፋኝ እርምጃዎችን እየወሰዱ መሆኑን የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች መመዝገባቸውን አምነስቲ አጋልጧል።
4 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና ዳሰሳ) በኢትዮጵያ እና በአሜሪካ መንግስት መካከል የተፈረመው የ1.616 ቢሊዮን ዶላር የሕዝብ ጤና ትብብር ስምምነት፣ የሀገሪቱን የፖሊሲ ነፃነት፣ ግልፅነት እና እውነተኛ አፈፃፀም አስመልክቶ አዳዲስ ሂሳዊ ጥያቄዎችን ማስነሳቱን አንድ አዲስ ጥናት ይፋ አደረገ። በእንግሊዙ ብሪስቶል ዩኒቨርሲቲ በጤና ኢኮኖሚክስ እና ፖሊሲ ትንተና ባለሙያ የቀረበው ይህ ጥናት፣ ስምምነቱ የሀገሪቱን የጤና ዘርፍ ያጠናክራል ተብሎ ቢነገርለትም፣ ከጎረቤት ሀገራት ተሞክሮ እና ከሀገር ውስጥ ነባራዊ ሁኔታ አኳያ በርካታ የትኩረት ክፍተቶች እንዳሉበት አመልክቷል።
የስምምነቱ ዝርዝር እና የኬንያ ንፅፅር
በታህሳስ 2018 (ዲሴምበር 2025) በጤና ሚኒስትሯ ዶ/ር መቅደስ ዳባ፣ በፋይናንስ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ እና በአሜሪካው አምባሳደር ኤርቪን ማሲንጋ መካከል የተፈረመው ይህ ስምምነት፣ አሜሪካ እስከ 1.166 ቢሊዮን ዶላር (ተጨማሪ የብቃት ድጋፍን ጨምሮ) እና ኢትዮጵያ 450 ሚሊዮን ዶላር በሀገር ውስጥ የሚሸፍኑበት ነው። ነገር ግን ጥናቱ እንደሚያሳየው፣ አጠቃላይ የህዝብ ብዛቷ የኢትዮጵያን ግማሽ ያህል የምትሆነው ጎረቤት ሀገር ኬንያ፣ በተመሳሳይ ጊዜ ከዩናይትድ ስቴትስ ጋር የ2.5 ቢሊዮን ዶላር ስምምነት ተፈራርማለች።
የኢትዮጵያ የህዝብ ብዛት እጅግ የበዛ ሆኖ እያለ፣ ለምን ከኬንያ በእጅጉ ያነሰ የፋይናንስ ድጋፍ ለመቀበል ተስማማች የሚለው ጥያቄ የሙያተኞችን ትኩረት ስቧል። የኢትዮጵያ ተደራዳሪዎች ከህዝብ ብዛታቸው አኳያ ከኬንያ እጥፍ ወይም እስከ 5 ቢሊዮን ዶላር የሚደርስ ድጋፍ ለምን አልጠየቁም የሚለውም ተነስቷል። ከዚህ በተጨማሪም በኬንያ የተደረገው ስምምነት በከፍተኛው ፍርድ ቤት እና በፓርላማ በግልፅነት፣ በህዝብ ተሳትፎ እና በጤና መረጃ ጥበቃ በኩል ተገቢው ምርመራ እንዲደረግበት መታገዱን የሚያስታውሰው ጥናት፣ የኢትዮጵያ ስምምነት በምን ያህል የፓርላማ እና የህግ ባለሙያዎች ምርመራና ይሁንታ አለፈ የሚለውን ይጠይቃል።
የሀገር ውስጥ የመድኃኒት ምርት እና የህዝብ ተቋማት እውነታ
ሌላው በጥናቱ የተነሳው አሳሳቢ ጉዳይ የመድኃኒት አቅርቦት እና የሀገር ውስጥ ምርት እውነታ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ በሐምሌ ወር ለፓርላማ ባደረጉት ንግግር የሀገር ውስጥ የመድኃኒት ምርት አቅም የሀገሪቱን 44 በመቶ ፍላጎት መሸፈን መቻሉን ገልጸው ነበር። ይሁን እንጂ በጥናቱ እንደተመላከተው፣ ይህ ቁጥር በወረቀት ላይ የሚታይ እንጂ በህዝብ የጤና ተቋማት ውስጥ ያለውን የመድኃኒት እጥረት አይገልጽም።
በጥራዝ ነጠቅ መረጃዎች እና በህሙማን ቅሬታዎች እንደታየው፣ የማህበረሰብ አቀፍ የጤና መድህን ክፍያ የሚከፍሉ ወደ 32 ሚሊዮን የሚጠጉ ዜጎች በመንግስት ሆስፒታሎች መድኃኒት በማጣታቸው ምክንያት ከኪሳቸው ተጨማሪ ገንዘብ አውጥተው ከግል ፋርማሲዎች ለመግዛት ይገደዳሉ። ይህም የመንግስት የሀገር ውስጥ ምርት አድጓል የሚለው መረጃ እና በምድር ላይ ያለው እውነታ አለመጣጣሙን ያሳያል።
የመልካም አስተዳደር እና የታማኝነት ጥያቄዎች
ጥናቱ ሲያጠቃልል ደግሞ የጤና ዘርፍ አመራር እና ስኬት መመዘን ያለበት በሚያምሩ ንግግሮች ወይም ስምምነቶች በመፈራረም ሳይሆን በዜጎች ህይወት ላይ በሚያመጣው ተጨባጭ ለውጥ መሆኑን ያሰምርበታል። የጤና ሚኒስቴር ለፓርላማ እና ለጠቅላይ ሚኒስትሩ የሚያቀርባቸው የቁጥር ሪፖርቶች እውነተኝነት በገለልተኛ አካል ሊረጋገጥ እንደሚገባ የተገለጸ ሲሆን፣ የመድኃኒት አቅርቦት እጥረትን ለማስወገድ እና በህዝብ የጤና ተቋማት ላይ እምነትን ለመመለስ ግልፅ አሰራር እና ቁጥጥር ሊኖር እንደሚገባ በጥናቱ አሳስቧል።
የስምምነቱ ዝርዝር እና የኬንያ ንፅፅር
በታህሳስ 2018 (ዲሴምበር 2025) በጤና ሚኒስትሯ ዶ/ር መቅደስ ዳባ፣ በፋይናንስ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ እና በአሜሪካው አምባሳደር ኤርቪን ማሲንጋ መካከል የተፈረመው ይህ ስምምነት፣ አሜሪካ እስከ 1.166 ቢሊዮን ዶላር (ተጨማሪ የብቃት ድጋፍን ጨምሮ) እና ኢትዮጵያ 450 ሚሊዮን ዶላር በሀገር ውስጥ የሚሸፍኑበት ነው። ነገር ግን ጥናቱ እንደሚያሳየው፣ አጠቃላይ የህዝብ ብዛቷ የኢትዮጵያን ግማሽ ያህል የምትሆነው ጎረቤት ሀገር ኬንያ፣ በተመሳሳይ ጊዜ ከዩናይትድ ስቴትስ ጋር የ2.5 ቢሊዮን ዶላር ስምምነት ተፈራርማለች።
የኢትዮጵያ የህዝብ ብዛት እጅግ የበዛ ሆኖ እያለ፣ ለምን ከኬንያ በእጅጉ ያነሰ የፋይናንስ ድጋፍ ለመቀበል ተስማማች የሚለው ጥያቄ የሙያተኞችን ትኩረት ስቧል። የኢትዮጵያ ተደራዳሪዎች ከህዝብ ብዛታቸው አኳያ ከኬንያ እጥፍ ወይም እስከ 5 ቢሊዮን ዶላር የሚደርስ ድጋፍ ለምን አልጠየቁም የሚለውም ተነስቷል። ከዚህ በተጨማሪም በኬንያ የተደረገው ስምምነት በከፍተኛው ፍርድ ቤት እና በፓርላማ በግልፅነት፣ በህዝብ ተሳትፎ እና በጤና መረጃ ጥበቃ በኩል ተገቢው ምርመራ እንዲደረግበት መታገዱን የሚያስታውሰው ጥናት፣ የኢትዮጵያ ስምምነት በምን ያህል የፓርላማ እና የህግ ባለሙያዎች ምርመራና ይሁንታ አለፈ የሚለውን ይጠይቃል።
የሀገር ውስጥ የመድኃኒት ምርት እና የህዝብ ተቋማት እውነታ
ሌላው በጥናቱ የተነሳው አሳሳቢ ጉዳይ የመድኃኒት አቅርቦት እና የሀገር ውስጥ ምርት እውነታ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ በሐምሌ ወር ለፓርላማ ባደረጉት ንግግር የሀገር ውስጥ የመድኃኒት ምርት አቅም የሀገሪቱን 44 በመቶ ፍላጎት መሸፈን መቻሉን ገልጸው ነበር። ይሁን እንጂ በጥናቱ እንደተመላከተው፣ ይህ ቁጥር በወረቀት ላይ የሚታይ እንጂ በህዝብ የጤና ተቋማት ውስጥ ያለውን የመድኃኒት እጥረት አይገልጽም።
በጥራዝ ነጠቅ መረጃዎች እና በህሙማን ቅሬታዎች እንደታየው፣ የማህበረሰብ አቀፍ የጤና መድህን ክፍያ የሚከፍሉ ወደ 32 ሚሊዮን የሚጠጉ ዜጎች በመንግስት ሆስፒታሎች መድኃኒት በማጣታቸው ምክንያት ከኪሳቸው ተጨማሪ ገንዘብ አውጥተው ከግል ፋርማሲዎች ለመግዛት ይገደዳሉ። ይህም የመንግስት የሀገር ውስጥ ምርት አድጓል የሚለው መረጃ እና በምድር ላይ ያለው እውነታ አለመጣጣሙን ያሳያል።
የመልካም አስተዳደር እና የታማኝነት ጥያቄዎች
ጥናቱ ሲያጠቃልል ደግሞ የጤና ዘርፍ አመራር እና ስኬት መመዘን ያለበት በሚያምሩ ንግግሮች ወይም ስምምነቶች በመፈራረም ሳይሆን በዜጎች ህይወት ላይ በሚያመጣው ተጨባጭ ለውጥ መሆኑን ያሰምርበታል። የጤና ሚኒስቴር ለፓርላማ እና ለጠቅላይ ሚኒስትሩ የሚያቀርባቸው የቁጥር ሪፖርቶች እውነተኝነት በገለልተኛ አካል ሊረጋገጥ እንደሚገባ የተገለጸ ሲሆን፣ የመድኃኒት አቅርቦት እጥረትን ለማስወገድ እና በህዝብ የጤና ተቋማት ላይ እምነትን ለመመለስ ግልፅ አሰራር እና ቁጥጥር ሊኖር እንደሚገባ በጥናቱ አሳስቧል።
4 days ago
ደህንነት ነኝ በማለት የማጭበርበር ወንጀል ሲፈፅም የነበረው ግለሰብ በእስራት እና በገንዘብ ተቀጣ
በአምቦ ከተማ ውስጥ ደህንነት ነኝ በማለት የማጭበርበር ወንጀል ሲፈፅም የነበረው ግለሰብ በእስራት እና በገንዘብ መቀጣቱ ተገልጿል ።የአምቦ ከተማ ፖሊስ ዋና መምሪያ የኮሚኒኬሽን ፅ/ቤት ሃላፊ ረዳት ኢንስፔክተር አቡሽ ማሞ ለብስራት ሬዲዮ እንደገለፁት ተከሳሽ ዘሪሁን ጉርሙ የሰላሳ ዓመት ግለሰብ ነው።
በከተማዋ ውስጥ በመዘዋወር " እኔ ደህንነት ነኝ " በወንጀል የተጠረጠሩ ሰዎችን አስፈታለሁ በማለት የማጭበርበር ወንጀል ፈፅሟል።ተከሳሹ አንዲት የአምቦ ከተማ ነዋሪ የሆነች ግለሰብን ባለቤትሽን ከተጠረጠረበት የወንጀል ድርጊት ነፃ እንዲወጣ አደርጋለሁ በማለት ከግለሰቧ ላይ 120 ሺህ ብር ሲቀበል በቁጥጥር ስር ውሏል ።
ፖሊስም በተከሳሹ ላይ አስፈላጊውን የምርመራ መዝገብ በተገቢው ማስረጃ በማጠናከር ለአቃቤህግ ልኳል። አቃቤ ህግም ከፖሊስ የተላከውን የምርመራ መዝገብ ተመልክቶ በአታላይነት ወንጀል ክስ መስርቶበታል።ክሱን የተመለከተው የአምቦ ከተማ ወረዳ ፍርድ ቤት ሃምሌ 17 ቀን 2018 ዓ.ም በዋለው ችሎት ተከሳሽ ዘሪሁን ጉርሙ የራሱን ማንነትና ሁኔታ በመሰወር፣ አሳሳች ነገሮችን በመናገር እና ደህንነት ነኝ በማለት በፈፀመው የማጭበርበር ወንጀል ጥፋተኛ መሆኑ ተረጋግጧል ።
በዚህም መሰረት በሁለት ዓመት ከ9ወር እስራትና በአንድ ሺህ ብር የገንዘብ መቀጮ ፣ እንዲቀጣ የተወሰነበት መሆኑን ረዳት ኢንስፔክተር አቡሽ ማሞ ጨምረው ለብስራት ሬዲዮ ገልፀዋል።
Seledadotio
Seledadotio
በአምቦ ከተማ ውስጥ ደህንነት ነኝ በማለት የማጭበርበር ወንጀል ሲፈፅም የነበረው ግለሰብ በእስራት እና በገንዘብ መቀጣቱ ተገልጿል ።የአምቦ ከተማ ፖሊስ ዋና መምሪያ የኮሚኒኬሽን ፅ/ቤት ሃላፊ ረዳት ኢንስፔክተር አቡሽ ማሞ ለብስራት ሬዲዮ እንደገለፁት ተከሳሽ ዘሪሁን ጉርሙ የሰላሳ ዓመት ግለሰብ ነው።
በከተማዋ ውስጥ በመዘዋወር " እኔ ደህንነት ነኝ " በወንጀል የተጠረጠሩ ሰዎችን አስፈታለሁ በማለት የማጭበርበር ወንጀል ፈፅሟል።ተከሳሹ አንዲት የአምቦ ከተማ ነዋሪ የሆነች ግለሰብን ባለቤትሽን ከተጠረጠረበት የወንጀል ድርጊት ነፃ እንዲወጣ አደርጋለሁ በማለት ከግለሰቧ ላይ 120 ሺህ ብር ሲቀበል በቁጥጥር ስር ውሏል ።
ፖሊስም በተከሳሹ ላይ አስፈላጊውን የምርመራ መዝገብ በተገቢው ማስረጃ በማጠናከር ለአቃቤህግ ልኳል። አቃቤ ህግም ከፖሊስ የተላከውን የምርመራ መዝገብ ተመልክቶ በአታላይነት ወንጀል ክስ መስርቶበታል።ክሱን የተመለከተው የአምቦ ከተማ ወረዳ ፍርድ ቤት ሃምሌ 17 ቀን 2018 ዓ.ም በዋለው ችሎት ተከሳሽ ዘሪሁን ጉርሙ የራሱን ማንነትና ሁኔታ በመሰወር፣ አሳሳች ነገሮችን በመናገር እና ደህንነት ነኝ በማለት በፈፀመው የማጭበርበር ወንጀል ጥፋተኛ መሆኑ ተረጋግጧል ።
በዚህም መሰረት በሁለት ዓመት ከ9ወር እስራትና በአንድ ሺህ ብር የገንዘብ መቀጮ ፣ እንዲቀጣ የተወሰነበት መሆኑን ረዳት ኢንስፔክተር አቡሽ ማሞ ጨምረው ለብስራት ሬዲዮ ገልፀዋል።
Seledadotio
Seledadotio
4 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) በፌንቴክ ኢንቨስትመንት የመኪና ማጭበርበር ወንጀል ጋር በተያያዘ ተጠርጥሮ በእስር ላይ የቆየው ቲክቶከር መንሱር ጀማል፣ የተፈቀደለትን የዋስትና ገንዘብ ከፍሎ ማምሻውን ከእስር በመለቀቅ ቤቱ መግባቱ ተሰማ። ይህንን ተከትሎም ተጠርጣሪው ቀሪ የፍርድ ቤት የህግ ሂደቶችን እና ክሱን በውጭ ሆኖ የሚከታተል ይሆናል።
ባለፈው ሳምንት አርብ ዕለት የሰበር ሰሚ ፍርድ ቤት ለቲክቶከሩ የ800 ሺህ ብር የዋስትና መብት መፍቀዱ ይታወሳል። የፍርድ ቤቱን ውሳኔ ተከትሎ ተጠርጣሪው ደስታ ቢሰማውም፣ የተጠየቀውን ከፍተኛ የዋስትና ገንዘብ ወዲያውኑ አቅርቦ መክፈል ባለመቻሉ ድንጋጤ ውስጥ ወድቆ እንደነበር የገንዘብ ማሰባሰብ ሂደቱን ያስተባበሩ ግለሰቦች ለ'ዘ-ሀበሻ' ገልጸዋል። ይህንን ክፍተት ለመሙላትም በፍጥነት ወደ መዋጮ ማሰባሰብ ስራ በመግባት ገንዘቡን አሟልተው ክፍያውን በመፈጸም ዛሬ ከእስር ሊያስፈቱት ችለዋል።
በዋስትና ገንዘብ ማሰባሰቡ ሂደት ማን ምን ያህል ገንዘብ እንዳዋጣ የሚያሳይ ስክሪን ሾትን የመሳሰሉ ማስረጃዎች ቢኖሩም፣ አስተዋጽኦ ያደረጉት ወገኖች ማንነታቸው በምስጢር እንዲያዝ መፈለጋቸው ታውቋል። ግለሰቦቹ ስማቸው እንዳይገለጽ እና እንዳይታወቅ የሚፈልጉበት ዋነኛ ምክንያት፣ በፌንቴክ ማጭበርበር ገንዘባቸውን ካጡ ተበዳዮች ሊሰነዘርብን ይችላል ከሚል የጥቃት ስጋት እና ፍራቻ አንጻር መሆኑ ተጠቁሟል።
ባለፈው ሳምንት አርብ ዕለት የሰበር ሰሚ ፍርድ ቤት ለቲክቶከሩ የ800 ሺህ ብር የዋስትና መብት መፍቀዱ ይታወሳል። የፍርድ ቤቱን ውሳኔ ተከትሎ ተጠርጣሪው ደስታ ቢሰማውም፣ የተጠየቀውን ከፍተኛ የዋስትና ገንዘብ ወዲያውኑ አቅርቦ መክፈል ባለመቻሉ ድንጋጤ ውስጥ ወድቆ እንደነበር የገንዘብ ማሰባሰብ ሂደቱን ያስተባበሩ ግለሰቦች ለ'ዘ-ሀበሻ' ገልጸዋል። ይህንን ክፍተት ለመሙላትም በፍጥነት ወደ መዋጮ ማሰባሰብ ስራ በመግባት ገንዘቡን አሟልተው ክፍያውን በመፈጸም ዛሬ ከእስር ሊያስፈቱት ችለዋል።
በዋስትና ገንዘብ ማሰባሰቡ ሂደት ማን ምን ያህል ገንዘብ እንዳዋጣ የሚያሳይ ስክሪን ሾትን የመሳሰሉ ማስረጃዎች ቢኖሩም፣ አስተዋጽኦ ያደረጉት ወገኖች ማንነታቸው በምስጢር እንዲያዝ መፈለጋቸው ታውቋል። ግለሰቦቹ ስማቸው እንዳይገለጽ እና እንዳይታወቅ የሚፈልጉበት ዋነኛ ምክንያት፣ በፌንቴክ ማጭበርበር ገንዘባቸውን ካጡ ተበዳዮች ሊሰነዘርብን ይችላል ከሚል የጥቃት ስጋት እና ፍራቻ አንጻር መሆኑ ተጠቁሟል።
4 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) በሁለተኛው የዶናልድ ትራምፕ የሥልጣን ዘመን፣ የዩናይትድ ስቴትስ የኢሚግሬሽን እና ጉምሩክ አስከባሪ ኤጀንሲ (ICE) በሀምሌ ወር ብቻ ከ46,000 በላይ ስደተኞችን በማሰር አዲስ ወርሃዊ ክብረ ወሰን አስመዝግቧል። ሲቢኤስ ኒውስ ያገኘው የውስጥ መረጃ እንደሚያሳየው፣ ኤጀንሲው አፈሳውን አድማስ በማስፋት በአውሮፕላን ማረፊያዎች፣ የኢሚግሬሽን ቢሮዎች እና በተለያዩ ማህበረሰቦች ውስጥ አጠናክሮ ቀጥሏል።
ይህ የሀምሌ ወር አሃዝ በሰኔ ወር ተመዝግቦ የነበረውን የ43,000 እስራት የሻረ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት በICE ማቆያ ማዕከላት ውስጥ የሚገኙ ታሳሪዎች ቁጥር 68,000 ደርሷል። የሀገር ውስጥ ደህንነት ሚኒስትር ማርክዌይን ሙሊን ተቋሙን ከተረከቡ ወዲህ፣ ኤጀንሲው ከሚዲያ እይታ ርቆ (በጸጥታ) ነገር ግን እጅግ በተጠናከረ መልኩ የትራምፕን "በታሪክ ትልቁን የሀገር ማስወጣት" ቃል ኪዳን እያስፈጸመ ይገኛል።
የኤጀንሲው ጠንካራ እርምጃዎች በአሜሪካ ውስጥ ከፍተኛ ውዝግቦችን እና ሰብዓዊ ስጋቶችን ማስነሳታቸውን ቀጥለዋል። በቅርቡ በቴክሳስ እና ሜይን የትራፊክ ፍተሻ ወቅት ሁለት ስደተኞች በICE አባላት መገደላቸውን ተከትሎ አፈሳው በጊዜያዊነት ተቋርጦ የነበረ ቢሆንም፣ በፕሬዝዳንት ትራምፕ ቀጥተኛ ጣልቃ ገብነት በ24 ሰዓታት ውስጥ ዳግም እንዲጀመር ተደርጓል።
ከዚህ በተጨማሪም ኤጀንሲው ከትራንስፖርት ደህንነት አስተዳደር (TSA) ጋር በመተባበር በአውሮፕላን ማረፊያዎች የሲቪል ልብስ በለበሱ አባላቱ የሚያደርገው አፈሳ ተቃውሞ እና ቁጣን አስነስቷል። ሁኔታውን ይበልጥ አሳሳቢ ያደረገው ደግሞ፣ አስተዳደሩ ከ300,000 በላይ ለሚሆኑ የሄይቲ ስደተኞች የተሰጠውን የጊዜያዊ የመኖሪያ ጥበቃ መብት (TPS) በመሰረዙ፣ በርካታ ማህበረሰቦችን በከፍተኛ ፍርሃት ውስጥ መክተቱ ነው።
የሀገር ውስጥ ደህንነት መምሪያው በሰጠው መግለጫ፣ ትራምፕ ዳግም ወደ ስልጣን ከመጡበት ጊዜ አንስቶ እስካሁን ከ985,000 በላይ ህገ-ወጥ ስደተኞችን ከሀገር ማስወጣቱን እና ከ1 ሚሊዮን በላይ የሚሆኑትን ደግሞ በቁጥጥር ስር ማዋሉን ይፋ አድርጓል። ሚኒስትሩ "መንገዶች ላይ ያለውን ሙቀት እየጨመርነው ነው፤ ህግ አስከባሪዎቻችን ስራቸውን እንዲሰሩ ሙሉ ስልጣን ስለሰጠናቸው ከምንጊዜውም በላይ ጠንክረን እየሰራን ነው" ሲሉ እርምጃውን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ አረጋግጠዋል።
ይህ የሀምሌ ወር አሃዝ በሰኔ ወር ተመዝግቦ የነበረውን የ43,000 እስራት የሻረ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት በICE ማቆያ ማዕከላት ውስጥ የሚገኙ ታሳሪዎች ቁጥር 68,000 ደርሷል። የሀገር ውስጥ ደህንነት ሚኒስትር ማርክዌይን ሙሊን ተቋሙን ከተረከቡ ወዲህ፣ ኤጀንሲው ከሚዲያ እይታ ርቆ (በጸጥታ) ነገር ግን እጅግ በተጠናከረ መልኩ የትራምፕን "በታሪክ ትልቁን የሀገር ማስወጣት" ቃል ኪዳን እያስፈጸመ ይገኛል።
የኤጀንሲው ጠንካራ እርምጃዎች በአሜሪካ ውስጥ ከፍተኛ ውዝግቦችን እና ሰብዓዊ ስጋቶችን ማስነሳታቸውን ቀጥለዋል። በቅርቡ በቴክሳስ እና ሜይን የትራፊክ ፍተሻ ወቅት ሁለት ስደተኞች በICE አባላት መገደላቸውን ተከትሎ አፈሳው በጊዜያዊነት ተቋርጦ የነበረ ቢሆንም፣ በፕሬዝዳንት ትራምፕ ቀጥተኛ ጣልቃ ገብነት በ24 ሰዓታት ውስጥ ዳግም እንዲጀመር ተደርጓል።
ከዚህ በተጨማሪም ኤጀንሲው ከትራንስፖርት ደህንነት አስተዳደር (TSA) ጋር በመተባበር በአውሮፕላን ማረፊያዎች የሲቪል ልብስ በለበሱ አባላቱ የሚያደርገው አፈሳ ተቃውሞ እና ቁጣን አስነስቷል። ሁኔታውን ይበልጥ አሳሳቢ ያደረገው ደግሞ፣ አስተዳደሩ ከ300,000 በላይ ለሚሆኑ የሄይቲ ስደተኞች የተሰጠውን የጊዜያዊ የመኖሪያ ጥበቃ መብት (TPS) በመሰረዙ፣ በርካታ ማህበረሰቦችን በከፍተኛ ፍርሃት ውስጥ መክተቱ ነው።
የሀገር ውስጥ ደህንነት መምሪያው በሰጠው መግለጫ፣ ትራምፕ ዳግም ወደ ስልጣን ከመጡበት ጊዜ አንስቶ እስካሁን ከ985,000 በላይ ህገ-ወጥ ስደተኞችን ከሀገር ማስወጣቱን እና ከ1 ሚሊዮን በላይ የሚሆኑትን ደግሞ በቁጥጥር ስር ማዋሉን ይፋ አድርጓል። ሚኒስትሩ "መንገዶች ላይ ያለውን ሙቀት እየጨመርነው ነው፤ ህግ አስከባሪዎቻችን ስራቸውን እንዲሰሩ ሙሉ ስልጣን ስለሰጠናቸው ከምንጊዜውም በላይ ጠንክረን እየሰራን ነው" ሲሉ እርምጃውን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ አረጋግጠዋል።
Sponsored by
Surafel
5 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና ዳሰሳ) የሶማሌላንድ የሀገርነት ጥያቄ እና አለም አቀፍ እውቅና የማግኘት ፍላጎት በዋናነት የተመሰረተው በቅኝ ግዛት ወቅት በነበራት ግልጽ ድንበር፣ እ.ኤ.አ. በ1960 ለተወሰኑ ቀናት አግኝታው በነበረው ነጻነት እና በ1991 ያወጀችው ነጻነት አዲስ የመገንጠል ጥያቄ ሳይሆን የነበረን ሉዓላዊነት የመመለስ እርምጃ ነው በሚለው መከራከሪያ ላይ ነው። እንግሊዝ ከ1884 እስከ 1886 በሰሜን ሶማሊያ ከሚገኙ የጎሳ መሪዎች ጋር ባደረገችው የስምምነት ውል መሰረት የሶማሌላንድን ግዛት የመሰረተች ሲሆን፣ የውጭ ድንበሮቿም ከፈረንሳይ፣ ጣሊያን እና ኢትዮጵያ ጋር በተደረጉ አለም አቀፍ ስምምነቶች የተከለሉ ነበሩ። ሰኔ 26 ቀን 1960 ከእንግሊዝ ቅኝ ግዛት ነጻነቷን የተቀዳጀችው ሶማሌላንድ፣ ከአምስት ቀናት በኋላ በፈቃደኝነት ከጣሊያን ሶማሊያ ጋር በመዋሃድ የሶማሊያ ሪፐብሊክን መስርታለች። ይሁን እንጂ የሶማሊያ ማዕከላዊ መንግስት በ1991 መውደቁን ተከትሎ፣ ሶማሌላንድ ከውህደቱ በፊት ወደ ነበራት ነጻነት መመለሷን በማወጅ የ1960ዋን ግዛቷን ይዛለች።
የሶማሌላንድ ዋነኛ የህግ መከራከሪያ አዲስ ነጻ የሚወጡ ሀገራት በቅኝ ግዛት ወቅት የነበራቸውን ድንበር ጠብቀው ሊቀጥሉ ይገባል የሚለው መርህ ነው። የአፍሪካ አንድነት ድርጅት በ1964ቱ የካይሮ ውሳኔው እንዲሁም የአፍሪካ ህብረት የመመስረቻ ሰነዱ ላይ አባል ሀገራት በነጻነት ጊዜ የነበራቸውን ድንበር ሊያከብሩ እንደሚገባ አስፍረዋል። በመሆኑም ሶማሌላንድ አለም አቀፍ እውቅና ማግኘቷ የቅኝ ግዛት ድንበርን ከመጠበቅ ባለፈ አዲስ ድንበር የማካለል ስራ አይደለም በማለት ትከራከራለች። አቋሟም ከዚህ ቀደም ሉዓላዊ ሀገር እንደነበረች፣ የ1960ውን ውህደት በራሷ ፈቃድ እንደፈጸመች እና የ1991ዱ እርምጃዋም የከሸፈን ውህደት ማፍረስ እንጂ አዲስ ግዛትን ከሶማሊያ መገንጠል አይደለም በሚሉ ሶስት ምሶሶዎች ላይ የቆመ ነው። ይህ አቀራረብ ሶማሌላንድን ምንም አይነት የቅኝ ግዛት ወይም አለም አቀፍ ድንበር መሰረት ከሌላቸው የመገንጠል ጥያቄዎች የተለየች ያደርጋታል።
የሶማሌላንድን ሁኔታ ከኤርትራ ጋር ማነጻጸር የጉዳዩን የዲፕሎማሲ ውስብስብነት በደንብ ያሳያል። ሁለቱም ግዛቶች የተለየ የቅኝ ግዛት ታሪክ፣ ከማዕከላዊ መንግስት ጋር የተደረገ የትጥቅ ትግል እና ከ1991 በኋላ ውጤታማ የሆነ ራስን በራስ የማስተዳደር ልምድ አላቸው። ይሁን እንጂ የኤርትራ የነጻነት ጥያቄ የኢትዮጵያን የሽግግር መንግስት ፈቃድ እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የህዝበ ውሳኔ ታዛቢነትን በማግኘቱ ፈጣን አለም አቀፍ እውቅናን ሊያጎናጽፋት ችሏል። በሶማሌላንድ በኩል ግን ጠንካራ ተቋማትን መገንባት እና ህዝበ ውሳኔ ማካሄድ ብትችልም፣ ከሶማሊያ መንግስት የተገኘ ስምምነትም ሆነ እንደ ኤርትራው አይነት አለም አቀፍ ድጋፍ ባለማግኘቷ የዲፕሎማሲ እውቅናው ሊዘገይባት ችሏል። ይህ የሚያሳየው ውጤታማ አስተዳደር እና ታሪካዊ ድንበር መኖር ብቻውን በቂ እንዳልሆነ እና እውቅና ማግኘት በስምምነት፣ በቀጠናዊ ፖለቲካ እና በዲፕሎማሲያዊ ድጋፍ ላይ በእጅጉ የተመሰረተ መሆኑን ነው።
የአፍሪካ ህብረት በ2005 ወደ አካባቢው አጣሪ ቡድን ልኮ የሶማሌላንድ ጥያቄ በቅኝ ግዛት ድንበር እና በቀድሞ ነጻነቷ ላይ የተመሰረተ ታሪካዊ መነሻ እንዳለው ቢገነዘብም፣ አሁንም ድረስ ለሶማሊያ ሉዓላዊነት እና የግዛት አንድነት ቅድሚያ መስጠትን መርጧል። በርካታ የአፍሪካ ሀገራት ሶማሌላንድን እውቅና መስጠት በሌሎች አካባቢዎች የመገንጠል ጥያቄዎችን ሊያነሳሳ ይችላል የሚል ስጋት አላቸው። ሶማሌላንድ በበኩሏ የድሮውን ድንበር መመለስ እንጂ አዲስ ድንበር መፍጠር አይደለም ስትል ምላሽ ትሰጣለች።
ሶማሌላንድ በቅኝ ግዛት ድንበር እና በቀድሞ ነጻነት ላይ የተመሰረተ ጠንካራ የህግ መከራከሪያ ብታቀርብም፣ የኤርትራን ተሞክሮ ስንመለከት የህግ ትንታኔ ብቻውን እውቅናን እንደማያመጣ መገንዘብ ይቻላል። ሶማሌላንድ ከሶማሊያ ጋር የደረሰችበት ምንም አይነት ስምምነት ባለመኖሩ፣ የእውቅና ጉዳይ አሁንም ድረስ አለም አቀፍ ተቋማት የድሮዋን ሉዓላዊ ሀገር ዳግም መመለስ አድርገው ይቀበሉታል ወይስ የሶማሊያን የግዛት አንድነት የሚፈታተን ድርጊት አድርገው ይቆጥሩታል የሚለው ጉዳይ የፈተና መድረክ ሆኖ ቀጥሏል።
የሶማሌላንድ ዋነኛ የህግ መከራከሪያ አዲስ ነጻ የሚወጡ ሀገራት በቅኝ ግዛት ወቅት የነበራቸውን ድንበር ጠብቀው ሊቀጥሉ ይገባል የሚለው መርህ ነው። የአፍሪካ አንድነት ድርጅት በ1964ቱ የካይሮ ውሳኔው እንዲሁም የአፍሪካ ህብረት የመመስረቻ ሰነዱ ላይ አባል ሀገራት በነጻነት ጊዜ የነበራቸውን ድንበር ሊያከብሩ እንደሚገባ አስፍረዋል። በመሆኑም ሶማሌላንድ አለም አቀፍ እውቅና ማግኘቷ የቅኝ ግዛት ድንበርን ከመጠበቅ ባለፈ አዲስ ድንበር የማካለል ስራ አይደለም በማለት ትከራከራለች። አቋሟም ከዚህ ቀደም ሉዓላዊ ሀገር እንደነበረች፣ የ1960ውን ውህደት በራሷ ፈቃድ እንደፈጸመች እና የ1991ዱ እርምጃዋም የከሸፈን ውህደት ማፍረስ እንጂ አዲስ ግዛትን ከሶማሊያ መገንጠል አይደለም በሚሉ ሶስት ምሶሶዎች ላይ የቆመ ነው። ይህ አቀራረብ ሶማሌላንድን ምንም አይነት የቅኝ ግዛት ወይም አለም አቀፍ ድንበር መሰረት ከሌላቸው የመገንጠል ጥያቄዎች የተለየች ያደርጋታል።
የሶማሌላንድን ሁኔታ ከኤርትራ ጋር ማነጻጸር የጉዳዩን የዲፕሎማሲ ውስብስብነት በደንብ ያሳያል። ሁለቱም ግዛቶች የተለየ የቅኝ ግዛት ታሪክ፣ ከማዕከላዊ መንግስት ጋር የተደረገ የትጥቅ ትግል እና ከ1991 በኋላ ውጤታማ የሆነ ራስን በራስ የማስተዳደር ልምድ አላቸው። ይሁን እንጂ የኤርትራ የነጻነት ጥያቄ የኢትዮጵያን የሽግግር መንግስት ፈቃድ እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የህዝበ ውሳኔ ታዛቢነትን በማግኘቱ ፈጣን አለም አቀፍ እውቅናን ሊያጎናጽፋት ችሏል። በሶማሌላንድ በኩል ግን ጠንካራ ተቋማትን መገንባት እና ህዝበ ውሳኔ ማካሄድ ብትችልም፣ ከሶማሊያ መንግስት የተገኘ ስምምነትም ሆነ እንደ ኤርትራው አይነት አለም አቀፍ ድጋፍ ባለማግኘቷ የዲፕሎማሲ እውቅናው ሊዘገይባት ችሏል። ይህ የሚያሳየው ውጤታማ አስተዳደር እና ታሪካዊ ድንበር መኖር ብቻውን በቂ እንዳልሆነ እና እውቅና ማግኘት በስምምነት፣ በቀጠናዊ ፖለቲካ እና በዲፕሎማሲያዊ ድጋፍ ላይ በእጅጉ የተመሰረተ መሆኑን ነው።
የአፍሪካ ህብረት በ2005 ወደ አካባቢው አጣሪ ቡድን ልኮ የሶማሌላንድ ጥያቄ በቅኝ ግዛት ድንበር እና በቀድሞ ነጻነቷ ላይ የተመሰረተ ታሪካዊ መነሻ እንዳለው ቢገነዘብም፣ አሁንም ድረስ ለሶማሊያ ሉዓላዊነት እና የግዛት አንድነት ቅድሚያ መስጠትን መርጧል። በርካታ የአፍሪካ ሀገራት ሶማሌላንድን እውቅና መስጠት በሌሎች አካባቢዎች የመገንጠል ጥያቄዎችን ሊያነሳሳ ይችላል የሚል ስጋት አላቸው። ሶማሌላንድ በበኩሏ የድሮውን ድንበር መመለስ እንጂ አዲስ ድንበር መፍጠር አይደለም ስትል ምላሽ ትሰጣለች።
ሶማሌላንድ በቅኝ ግዛት ድንበር እና በቀድሞ ነጻነት ላይ የተመሰረተ ጠንካራ የህግ መከራከሪያ ብታቀርብም፣ የኤርትራን ተሞክሮ ስንመለከት የህግ ትንታኔ ብቻውን እውቅናን እንደማያመጣ መገንዘብ ይቻላል። ሶማሌላንድ ከሶማሊያ ጋር የደረሰችበት ምንም አይነት ስምምነት ባለመኖሩ፣ የእውቅና ጉዳይ አሁንም ድረስ አለም አቀፍ ተቋማት የድሮዋን ሉዓላዊ ሀገር ዳግም መመለስ አድርገው ይቀበሉታል ወይስ የሶማሊያን የግዛት አንድነት የሚፈታተን ድርጊት አድርገው ይቆጥሩታል የሚለው ጉዳይ የፈተና መድረክ ሆኖ ቀጥሏል።
5 days ago
20,000 ዶላር ዋስትና‼️
አሜሪካ የቪዛ ዋስትና ክፍያን ቋሚ አደረገች፣ ተጓዦች እስከ 20 ሺህ ዶላር ይጠየቃሉ።
የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ከኢትዮጵያ እና ከሌሎች 30 የአፍሪካ ሀገራት ጨምሮ የ50 ሀገራት ዜጎች ወደ ሀገሪቱ ለንግድና ለጉብኝት (B1/B2) ቪዛ ሲያመልክቱ እስከ 20 ሺህ የአሜሪካ ዶላር የቪዛ ዋስትና (Visa Bond) ማስያዝ የሚያስገድደውን መመሪያ በቋሚነት ማጽደቁን አስታወቀ።
እንደ አዲሱ መመሪያ አሰራር፣ ተጓዦች የተሰጣቸውን የቪዛ ጊዜ ሳያሳልፉ እና የሀገሪቱን ህግ አክብረው ከተመለሱ ያስያዙት ገንዘብ ሙሉ በሙሉ ተመላሽ ይደረግላቸዋል። ነገር ግን ከተፈቀደላቸው ጊዜ በላይ የሚቆዩ ወይም የቪዛ ደንብ የሚጥሱ ከሆነ ያስያዙት ገንዘብ ለመንግስት ገቢ እንደሚሆን ተገልጻል።
ይህ አሰራር ቀደም ሲል ለሙከራ ትግበራ ተዘርግቶ የነበረ ሲሆን፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ባደረገው ግምገማ ከቪዛ ጊዜ በላይ የመቆየት ችግርን በመቀነስ ረገድ ውጤታማ ሆኖ በመገኘቱ በቋሚነት ስራ ላይ እንዲውል ተወስኗል። የቆንስላ ክፍሎች እንደ አመልካቾቹ ሁኔታ ከ10 ሺህ፣ 15 ሺህ እስከ 20 ሺህ ዶላር የሚደርስ ገንዘብ በዋስትና መልክ እንዲያዝ የመወሰን ስልጣን ተሰጥቷቸዋል።
በዚህ መመሪያ ውስጥ የተካተቱት የአፍሪካ ሀገራት ኢትዮጵያ፣ ናይጄሪያ፣ አልጄሪያ፣ አንጎላ፣ ቤኒን፣ ቦትስዋና፣ ቡሩንዲ፣ ኬፕ ቨርዴ፣ ማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ፣ ኮትዲቯር፣ ጅቡቲ፣ ጋቦን፣ ጋምቢያ፣ ጊኒ፣ ጊኒ ቢሳው፣ ሌሶቶ፣ ማላዊ፣ ሞሪታኒያ፣ ሞሪሸስ፣ ሞዛምቢክ፣ ናሚቢያ፣ ሳኦ ቶሜ እና ፕሪንሲፔ፣ ሴኔጋል፣ ሲሼልስ፣ ታንዛኒያ፣ ቶጎ፣ ቱኒዚያ፣ ኡጋንዳ፣ ዛምቢያ እና ዚምባብዌ ናቸው።
Seledadotio
Seledadotio
አሜሪካ የቪዛ ዋስትና ክፍያን ቋሚ አደረገች፣ ተጓዦች እስከ 20 ሺህ ዶላር ይጠየቃሉ።
የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ከኢትዮጵያ እና ከሌሎች 30 የአፍሪካ ሀገራት ጨምሮ የ50 ሀገራት ዜጎች ወደ ሀገሪቱ ለንግድና ለጉብኝት (B1/B2) ቪዛ ሲያመልክቱ እስከ 20 ሺህ የአሜሪካ ዶላር የቪዛ ዋስትና (Visa Bond) ማስያዝ የሚያስገድደውን መመሪያ በቋሚነት ማጽደቁን አስታወቀ።
እንደ አዲሱ መመሪያ አሰራር፣ ተጓዦች የተሰጣቸውን የቪዛ ጊዜ ሳያሳልፉ እና የሀገሪቱን ህግ አክብረው ከተመለሱ ያስያዙት ገንዘብ ሙሉ በሙሉ ተመላሽ ይደረግላቸዋል። ነገር ግን ከተፈቀደላቸው ጊዜ በላይ የሚቆዩ ወይም የቪዛ ደንብ የሚጥሱ ከሆነ ያስያዙት ገንዘብ ለመንግስት ገቢ እንደሚሆን ተገልጻል።
ይህ አሰራር ቀደም ሲል ለሙከራ ትግበራ ተዘርግቶ የነበረ ሲሆን፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ባደረገው ግምገማ ከቪዛ ጊዜ በላይ የመቆየት ችግርን በመቀነስ ረገድ ውጤታማ ሆኖ በመገኘቱ በቋሚነት ስራ ላይ እንዲውል ተወስኗል። የቆንስላ ክፍሎች እንደ አመልካቾቹ ሁኔታ ከ10 ሺህ፣ 15 ሺህ እስከ 20 ሺህ ዶላር የሚደርስ ገንዘብ በዋስትና መልክ እንዲያዝ የመወሰን ስልጣን ተሰጥቷቸዋል።
በዚህ መመሪያ ውስጥ የተካተቱት የአፍሪካ ሀገራት ኢትዮጵያ፣ ናይጄሪያ፣ አልጄሪያ፣ አንጎላ፣ ቤኒን፣ ቦትስዋና፣ ቡሩንዲ፣ ኬፕ ቨርዴ፣ ማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ፣ ኮትዲቯር፣ ጅቡቲ፣ ጋቦን፣ ጋምቢያ፣ ጊኒ፣ ጊኒ ቢሳው፣ ሌሶቶ፣ ማላዊ፣ ሞሪታኒያ፣ ሞሪሸስ፣ ሞዛምቢክ፣ ናሚቢያ፣ ሳኦ ቶሜ እና ፕሪንሲፔ፣ ሴኔጋል፣ ሲሼልስ፣ ታንዛኒያ፣ ቶጎ፣ ቱኒዚያ፣ ኡጋንዳ፣ ዛምቢያ እና ዚምባብዌ ናቸው።
Seledadotio
Seledadotio
6 days ago
አሜሪካ የቪዛ ዋስትና ክፍያን ቋሚ አደረገች፣ ተጓዦች እስከ 20 ሺህ ዶላር ይጠየቃሉ!
#fastmereja I የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ከኢትዮጵያ እና ከሌሎች 30 የአፍሪካ ሀገራት ጨምሮ የ50 ሀገራት ዜጎች ወደ ሀገሪቱ ለንግድና ለጉብኝት (B1/B2) ቪዛ ሲያመልክቱ እስከ 20 ሺህ የአሜሪካ ዶላር የቪዛ ዋስትና (Visa Bond) ማስያዝ የሚያስገድደውን መመሪያ በቋሚነት ማጽደቁን አስታወቀ።
ቀን፦ ነሐሴ 1 ቀን 2018 ዓ.ም. (August 1, 2026)
እንደ አዲሱ መመሪያ አሰራር፣ ተጓዦች የተሰጣቸውን የቪዛ ጊዜ ሳያሳልፉ እና የሀገሪቱን ህግ አክብረው ከተመለሱ ያስያዙት ገንዘብ ሙሉ በሙሉ ተመላሽ ይደረግላቸዋል። ነገር ግን ከተፈቀደላቸው ጊዜ በላይ የሚቆዩ ወይም የቪዛ ደንብ የሚጥሱ ከሆነ ያስያዙት ገንዘብ ለመንግስት ገቢ እንደሚሆን ተገልጻል።
ይህ አሰራር ቀደም ሲል ለሙከራ ትግበራ ተዘርግቶ የነበረ ሲሆን፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ባደረገው ግምገማ ከቪዛ ጊዜ በላይ የመቆየት ችግርን በመቀነስ ረገድ ውጤታማ ሆኖ በመገኘቱ በቋሚነት ስራ ላይ እንዲውል ተወስኗል። የቆንስላ ክፍሎች እንደ አመልካቾቹ ሁኔታ ከ10 ሺህ፣ 15 ሺህ እስከ 20 ሺህ ዶላር የሚደርስ ገንዘብ በዋስትና መልክ እንዲያዝ የመወሰን ስልጣን ተሰጥቷቸዋል።
በዚህ መመሪያ ውስጥ የተካተቱት የአፍሪካ ሀገራት ኢትዮጵያ፣ ናይጄሪያ፣ አልጄሪያ፣ አንጎላ፣ ቤኒን፣ ቦትስዋና፣ ቡሩንዲ፣ ኬፕ ቨርዴ፣ ማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ፣ ኮትዲቯር፣ ጅቡቲ፣ ጋቦን፣ ጋምቢያ፣ ጊኒ፣ ጊኒ ቢሳው፣ ሌሶቶ፣ ማላዊ፣ ሞሪታኒያ፣ ሞሪሸስ፣ ሞዛምቢክ፣ ናሚቢያ፣ ሳኦ ቶሜ እና ፕሪንሲፔ፣ ሴኔጋል፣ ሲሼልስ፣ ታንዛኒያ፣ ቶጎ፣ ቱኒዚያ፣ ኡጋንዳ፣ ዛምቢያ እና ዚምባብዌ ናቸው።
የአሜሪካ ባለስልጣናት እርምጃው የህገ-ወጥ ስደተኞችን ቁጥር እና የቪዛ ጊዜ ማለፍን ለመግታት ያለመ ነው ሲሉ ቢገልጹም፣ የስደት ህግ አዋቂዎችና የሰብአዊ መብት ተሟጋቾች ግን አሰራሩ ህጋዊ ተጓዦችን እንደሚያሰናክልና ከፍተኛ የፋይናንስ ጫና እንደሚፈጥር በመግለጽ ላይ ይገኛሉ።
#fastmereja I የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ከኢትዮጵያ እና ከሌሎች 30 የአፍሪካ ሀገራት ጨምሮ የ50 ሀገራት ዜጎች ወደ ሀገሪቱ ለንግድና ለጉብኝት (B1/B2) ቪዛ ሲያመልክቱ እስከ 20 ሺህ የአሜሪካ ዶላር የቪዛ ዋስትና (Visa Bond) ማስያዝ የሚያስገድደውን መመሪያ በቋሚነት ማጽደቁን አስታወቀ።
ቀን፦ ነሐሴ 1 ቀን 2018 ዓ.ም. (August 1, 2026)
እንደ አዲሱ መመሪያ አሰራር፣ ተጓዦች የተሰጣቸውን የቪዛ ጊዜ ሳያሳልፉ እና የሀገሪቱን ህግ አክብረው ከተመለሱ ያስያዙት ገንዘብ ሙሉ በሙሉ ተመላሽ ይደረግላቸዋል። ነገር ግን ከተፈቀደላቸው ጊዜ በላይ የሚቆዩ ወይም የቪዛ ደንብ የሚጥሱ ከሆነ ያስያዙት ገንዘብ ለመንግስት ገቢ እንደሚሆን ተገልጻል።
ይህ አሰራር ቀደም ሲል ለሙከራ ትግበራ ተዘርግቶ የነበረ ሲሆን፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ባደረገው ግምገማ ከቪዛ ጊዜ በላይ የመቆየት ችግርን በመቀነስ ረገድ ውጤታማ ሆኖ በመገኘቱ በቋሚነት ስራ ላይ እንዲውል ተወስኗል። የቆንስላ ክፍሎች እንደ አመልካቾቹ ሁኔታ ከ10 ሺህ፣ 15 ሺህ እስከ 20 ሺህ ዶላር የሚደርስ ገንዘብ በዋስትና መልክ እንዲያዝ የመወሰን ስልጣን ተሰጥቷቸዋል።
በዚህ መመሪያ ውስጥ የተካተቱት የአፍሪካ ሀገራት ኢትዮጵያ፣ ናይጄሪያ፣ አልጄሪያ፣ አንጎላ፣ ቤኒን፣ ቦትስዋና፣ ቡሩንዲ፣ ኬፕ ቨርዴ፣ ማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ፣ ኮትዲቯር፣ ጅቡቲ፣ ጋቦን፣ ጋምቢያ፣ ጊኒ፣ ጊኒ ቢሳው፣ ሌሶቶ፣ ማላዊ፣ ሞሪታኒያ፣ ሞሪሸስ፣ ሞዛምቢክ፣ ናሚቢያ፣ ሳኦ ቶሜ እና ፕሪንሲፔ፣ ሴኔጋል፣ ሲሼልስ፣ ታንዛኒያ፣ ቶጎ፣ ቱኒዚያ፣ ኡጋንዳ፣ ዛምቢያ እና ዚምባብዌ ናቸው።
የአሜሪካ ባለስልጣናት እርምጃው የህገ-ወጥ ስደተኞችን ቁጥር እና የቪዛ ጊዜ ማለፍን ለመግታት ያለመ ነው ሲሉ ቢገልጹም፣ የስደት ህግ አዋቂዎችና የሰብአዊ መብት ተሟጋቾች ግን አሰራሩ ህጋዊ ተጓዦችን እንደሚያሰናክልና ከፍተኛ የፋይናንስ ጫና እንደሚፈጥር በመግለጽ ላይ ይገኛሉ።
Comments