2 days ago
የኢትዮጵያን ዴሞክራሲ ወደ አዲስ ምዕራፍ ያሸጋገረው ምርጫ …
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 26፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የኢትዮጵያን የዴሞክራሲና የሀገረ መንግሥት ግንባታ ወደ አዲስ ምዕራፍ ያሸጋገረ ነው አሉ የህግና ፌደራሊዝም ባለሙያ በላይ ወዲሻ።
ባለሙያው ከፋና ፖድካስት ጋር በነበራቸው ቆይታ፤ ዜጎች ከማለዳው 12 ሰዓት ጀምሮ እስከ ምሽቱ 6 ሰዓት በሰላማዊ መንገድ ድምፅ መስጠታቸውን አስታውሰዋል።
ይህም በሀገሪቱ የፖለቲካ ንቃትና የዴሞክራሲ ባህል መዳበሩን የሚያሳይ ነው ብለዋል።
የዘንድሮው የፖለቲካ ፓርቲዎች ቅስቀሳ፣ የምርጫ ቦርድ ዝግጅትና በዕለቱ የምርጫ ሂደት የታየው መነቃቃት የፖለቲካ ምህዳሩን በማስፋት ረገድ አዎንታዊ ሚና እንደነበረው ጠቅሰዋል።
የመገናኛ ብዙሃን እና የሲቪክ ማህበራት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከታቸውን ገልጸው፤ ጠቅላላ ውጤቱ ይፋ እስኪሆን መጠበቅ የሁሉም ፖለቲካ ፓርቲዎች እና የዜጎች ቀጥተኛ ኃላፊነት ነው ብለዋል።
ፓርቲዎች ውጤቱ ይፋ ሳይሆን ከመገመት ተቆጥበው ሂደቱን በትዕግስት መጠበቅ እስኪገለጽ መጠበቅ ወሳኝ መሆኑን አንስተዋል።
በውጤቱ ፓርቲ ሳይሆን ኢትዮጵያ ናት የምታሸንፈው ያሉት ባለሙያው፤ ፓርቲዎች ውጤቱን በፀጋ ተቀብለው በሀገር ልማት እና ግንባታ ላይ በንቃት መሳተፍ ይገባቸዋል ሲሉ ገልጸዋል።
የምርጫው በሰላም መጠናቀቅ ለሀገር ግንባታ ዋስትና መሆኑን ጠቅሰው፤ በህዝብ ድምፅ የበላይነት ያገኘው ፓርቲ ለሕዝብ የገባውን ቃል በታማኝነት የመፈጸም ኃላፊነት እንዳለበትም ጠቁመዋል።
ምርጫው የሕግ የበላይነትን ለማረጋገጥ፣ ተዓማኒነትን ለመገንባት እና የኢትዮጵያን የሀገር ግንባታ ጉዞ ለማፅናት ትልቅ ስኬት መሆኑንም አንስተዋል።
በቅድስት ዘውዱ
የህግና ፌደራሊዝም ባለሞያ በላይ ወዲሻ
ከፋና ፖድካስት ጋር ያደረገውን ቆይታ ለመከታተል ማስፈንጠሪያውን ይጫኑ https://youtu.be/jUX8tmYTs...
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 26፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የኢትዮጵያን የዴሞክራሲና የሀገረ መንግሥት ግንባታ ወደ አዲስ ምዕራፍ ያሸጋገረ ነው አሉ የህግና ፌደራሊዝም ባለሙያ በላይ ወዲሻ።
ባለሙያው ከፋና ፖድካስት ጋር በነበራቸው ቆይታ፤ ዜጎች ከማለዳው 12 ሰዓት ጀምሮ እስከ ምሽቱ 6 ሰዓት በሰላማዊ መንገድ ድምፅ መስጠታቸውን አስታውሰዋል።
ይህም በሀገሪቱ የፖለቲካ ንቃትና የዴሞክራሲ ባህል መዳበሩን የሚያሳይ ነው ብለዋል።
የዘንድሮው የፖለቲካ ፓርቲዎች ቅስቀሳ፣ የምርጫ ቦርድ ዝግጅትና በዕለቱ የምርጫ ሂደት የታየው መነቃቃት የፖለቲካ ምህዳሩን በማስፋት ረገድ አዎንታዊ ሚና እንደነበረው ጠቅሰዋል።
የመገናኛ ብዙሃን እና የሲቪክ ማህበራት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከታቸውን ገልጸው፤ ጠቅላላ ውጤቱ ይፋ እስኪሆን መጠበቅ የሁሉም ፖለቲካ ፓርቲዎች እና የዜጎች ቀጥተኛ ኃላፊነት ነው ብለዋል።
ፓርቲዎች ውጤቱ ይፋ ሳይሆን ከመገመት ተቆጥበው ሂደቱን በትዕግስት መጠበቅ እስኪገለጽ መጠበቅ ወሳኝ መሆኑን አንስተዋል።
በውጤቱ ፓርቲ ሳይሆን ኢትዮጵያ ናት የምታሸንፈው ያሉት ባለሙያው፤ ፓርቲዎች ውጤቱን በፀጋ ተቀብለው በሀገር ልማት እና ግንባታ ላይ በንቃት መሳተፍ ይገባቸዋል ሲሉ ገልጸዋል።
የምርጫው በሰላም መጠናቀቅ ለሀገር ግንባታ ዋስትና መሆኑን ጠቅሰው፤ በህዝብ ድምፅ የበላይነት ያገኘው ፓርቲ ለሕዝብ የገባውን ቃል በታማኝነት የመፈጸም ኃላፊነት እንዳለበትም ጠቁመዋል።
ምርጫው የሕግ የበላይነትን ለማረጋገጥ፣ ተዓማኒነትን ለመገንባት እና የኢትዮጵያን የሀገር ግንባታ ጉዞ ለማፅናት ትልቅ ስኬት መሆኑንም አንስተዋል።
በቅድስት ዘውዱ
የህግና ፌደራሊዝም ባለሞያ በላይ ወዲሻ
ከፋና ፖድካስት ጋር ያደረገውን ቆይታ ለመከታተል ማስፈንጠሪያውን ይጫኑ https://youtu.be/jUX8tmYTs...
2 days ago
ሰላም! እንደምን አደራችሁ?
ለቀጣይ አምስት ዓመታት የሚመራቸውን መንግሥት ለመምረጥ ኢትዮጵያውያን ግንቦት 24 ቀን ከማለዳ ጀምሮ እስከ ሌሊት ድምፃቸውን ሰጥተዋል።
ዜጎች በየአካባቢው በሚገኙ የምርጫ ጣቢያዎች ድምፅ የሰጡበት ይህ ሂደት÷ ኢትዮጵያውያን ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታና ለሀገረ መንግሥት ምስረታ ያላቸውን ፅኑ ቁርጠኝነት በተግባር ያሳዩበት ሆኖ አልፏል።
በሚሊየን የሚቆጠሩ መራጮች በነቂስ ወጥተው ዝናብና ጸሐይን እንዲሁም ከተለያዩ አካላት የሚነዙ የፕሮፓጋንዳ ዘመቻዎችንና ዛቻዎችን ሳያዳምጡ በረጃጅም ሰልፎች ተሰልፈው ውሳኔያቸውን አስተላልፈዋል።
በሕመም አልጋ ላይ የነበሩ ከሕመማቸው ጋር እየታገሉ፣ ሐዘን የገጠማቸውም ከሐዘናቸው ተነስተው በመውጣት ለነጋቸው የሚበጀውን ድምፅ የሰጡበት ዕለት ነው ግንቦት 24።
በዚህ ታሪካዊ ሂደት ላይ ለመሳተፍ በሚያስችል ዕድሜ ላይ የሚገኙ ከ54 ሚሊየን በላይ ዜጎች ተመዝግበው ከ10 ሺህ በላይ የፖለቲካ ፓርቲ ዕጩዎችና 80 የግል ዕጩዎች በተወዳደሩበት ምርጫ ድምጻቸውን በመስጠት ወሳኝ ሚና ተጫውተዋል።
የምርጫውን ግልጽነት፣ አሳታፊነትና ተዓማኒነት ከፍ ለማድረግ የተለያዩ ባለድርሻ አካላት የተሳተፉ ሲሆን÷ ከእነዚህም መካከል ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ወሳኝ ሚና ያላቸውና ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ፈቃድ ያገኙ 68 የመገናኛ ብዙኃን ተሰማርተዋል፤ ከእነዚህ ውስጥ 12ቱ የውጭ መገናኛ ብዙኃን ናቸው።
በተጨማሪም ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች የድምፅ አሰጣጥና የውጤት ቆጠራ ሂደቱን በቅርበት ለመከታተል ከ250 ሺህ በላይ ተወካዮቻቸውን በየምርጫ ጣቢያዎቹ መድበዋል።
በሌላ በኩል የኬንያ ቀድሞ ፕሬዚዳንት ኡሁሩ ኬንያታ የሚመራውና 59 አባላትን የያዘው የአፍሪካ ሕብረት የምርጫ ታዛቢ ቡድን እንዲሁም 26 አባላትን ያሰማራው የምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት ባለሥልጣን (ኢጋድ) በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች በመሰማራት ሂደቱን በንቃት ታዝበዋል።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ በሰጡት መግለጫ÷ የምርጫው ድምፅ የመስጠት ሂደት በስኬት መጠናቀቁንና በየምርጫ ጣቢያዎቹ የምርጫ ውጤቶችን ለሕዝብ የመለጠፍ ሥራዎች በይፋ መከናወናቸውን አረጋግጠዋል።
ይህም ኢትዮጵያ የራሷን ዕድል ለመወሰን መካሪና ገሳጭ እንደማያስፈልጋት በድጋሚ ያሳየበት ነው።
በድምፅ መስጫው ዕለት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከመራጩ ሕዝብ በላይ የተመራጮች ጉዳይና ኃላፊነት ይበልጥ እንደሚያሳስባቸው መግለጻቸው ይታወሳል።
በመሆኑም ሕዝብ ያሳየውን ፅኑ እምነትና የዴሞክራሲ ፍላጎት ሳይሸረሽር፣ በታማኝነትና በንጹሕ ልብ ማገልገል የነገው መንግሥት ቀዳሚ የቤት ሥራ እንደሚሆን ጠቅላይ ሚኒስትሩ አጽንዖት ሰጥተዋል።
የሕዝቡን ሕይወት የሚነካና የሀገሪቱን የነገ ዕጣ ፈንታ የሚወስን እውነተኛ ለውጥ ማምጣት የሚቻለውም ተመራጮች የተጣለባቸውን ታሪካዊ ኃላፊነት በትክክል ተረድተው ሲሰናዱ ብቻ በመሆኑ የኢትዮጵያ ቀጣይ አምስት ዓመታት ጉዞ በዚሁ የተመራጮች የዝግጁነት ሚዛን ላይ የሚያርፍ ይሆናል።
ኢትዮጵያ መርጣለች፤ ኢትዮጵያ አሸንፋለች!!
ለቀጣይ አምስት ዓመታት የሚመራቸውን መንግሥት ለመምረጥ ኢትዮጵያውያን ግንቦት 24 ቀን ከማለዳ ጀምሮ እስከ ሌሊት ድምፃቸውን ሰጥተዋል።
ዜጎች በየአካባቢው በሚገኙ የምርጫ ጣቢያዎች ድምፅ የሰጡበት ይህ ሂደት÷ ኢትዮጵያውያን ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታና ለሀገረ መንግሥት ምስረታ ያላቸውን ፅኑ ቁርጠኝነት በተግባር ያሳዩበት ሆኖ አልፏል።
በሚሊየን የሚቆጠሩ መራጮች በነቂስ ወጥተው ዝናብና ጸሐይን እንዲሁም ከተለያዩ አካላት የሚነዙ የፕሮፓጋንዳ ዘመቻዎችንና ዛቻዎችን ሳያዳምጡ በረጃጅም ሰልፎች ተሰልፈው ውሳኔያቸውን አስተላልፈዋል።
በሕመም አልጋ ላይ የነበሩ ከሕመማቸው ጋር እየታገሉ፣ ሐዘን የገጠማቸውም ከሐዘናቸው ተነስተው በመውጣት ለነጋቸው የሚበጀውን ድምፅ የሰጡበት ዕለት ነው ግንቦት 24።
በዚህ ታሪካዊ ሂደት ላይ ለመሳተፍ በሚያስችል ዕድሜ ላይ የሚገኙ ከ54 ሚሊየን በላይ ዜጎች ተመዝግበው ከ10 ሺህ በላይ የፖለቲካ ፓርቲ ዕጩዎችና 80 የግል ዕጩዎች በተወዳደሩበት ምርጫ ድምጻቸውን በመስጠት ወሳኝ ሚና ተጫውተዋል።
የምርጫውን ግልጽነት፣ አሳታፊነትና ተዓማኒነት ከፍ ለማድረግ የተለያዩ ባለድርሻ አካላት የተሳተፉ ሲሆን÷ ከእነዚህም መካከል ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ወሳኝ ሚና ያላቸውና ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ፈቃድ ያገኙ 68 የመገናኛ ብዙኃን ተሰማርተዋል፤ ከእነዚህ ውስጥ 12ቱ የውጭ መገናኛ ብዙኃን ናቸው።
በተጨማሪም ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች የድምፅ አሰጣጥና የውጤት ቆጠራ ሂደቱን በቅርበት ለመከታተል ከ250 ሺህ በላይ ተወካዮቻቸውን በየምርጫ ጣቢያዎቹ መድበዋል።
በሌላ በኩል የኬንያ ቀድሞ ፕሬዚዳንት ኡሁሩ ኬንያታ የሚመራውና 59 አባላትን የያዘው የአፍሪካ ሕብረት የምርጫ ታዛቢ ቡድን እንዲሁም 26 አባላትን ያሰማራው የምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት ባለሥልጣን (ኢጋድ) በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች በመሰማራት ሂደቱን በንቃት ታዝበዋል።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ በሰጡት መግለጫ÷ የምርጫው ድምፅ የመስጠት ሂደት በስኬት መጠናቀቁንና በየምርጫ ጣቢያዎቹ የምርጫ ውጤቶችን ለሕዝብ የመለጠፍ ሥራዎች በይፋ መከናወናቸውን አረጋግጠዋል።
ይህም ኢትዮጵያ የራሷን ዕድል ለመወሰን መካሪና ገሳጭ እንደማያስፈልጋት በድጋሚ ያሳየበት ነው።
በድምፅ መስጫው ዕለት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከመራጩ ሕዝብ በላይ የተመራጮች ጉዳይና ኃላፊነት ይበልጥ እንደሚያሳስባቸው መግለጻቸው ይታወሳል።
በመሆኑም ሕዝብ ያሳየውን ፅኑ እምነትና የዴሞክራሲ ፍላጎት ሳይሸረሽር፣ በታማኝነትና በንጹሕ ልብ ማገልገል የነገው መንግሥት ቀዳሚ የቤት ሥራ እንደሚሆን ጠቅላይ ሚኒስትሩ አጽንዖት ሰጥተዋል።
የሕዝቡን ሕይወት የሚነካና የሀገሪቱን የነገ ዕጣ ፈንታ የሚወስን እውነተኛ ለውጥ ማምጣት የሚቻለውም ተመራጮች የተጣለባቸውን ታሪካዊ ኃላፊነት በትክክል ተረድተው ሲሰናዱ ብቻ በመሆኑ የኢትዮጵያ ቀጣይ አምስት ዓመታት ጉዞ በዚሁ የተመራጮች የዝግጁነት ሚዛን ላይ የሚያርፍ ይሆናል።
ኢትዮጵያ መርጣለች፤ ኢትዮጵያ አሸንፋለች!!
3 days ago
"ከፈጣሪ በቀር ሕዝባችንን አሟልቶ ሊያውቅ እና ሊገመግም የሚችል ማን ነው?"
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የኢትዮጵያውያንን ፅናት፣ ሀገር ወዳድነት እና ለሀገረ-መንግሥት ግንባታ ያለችውን ቁርጠኝነት የገለጹበት መልዕክት።
#ebc #ethiopia #pmabiyahmed #ethiopiaprevails
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የኢትዮጵያውያንን ፅናት፣ ሀገር ወዳድነት እና ለሀገረ-መንግሥት ግንባታ ያለችውን ቁርጠኝነት የገለጹበት መልዕክት።
#ebc #ethiopia #pmabiyahmed #ethiopiaprevails
10 days ago
የዘንድሮው ሀገራዊ ምርጫ የሀገረ-መንግሥት ሥርዓታችን መሠረት ነው፦ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
#ethiopia | የዘንድሮው ሀገራዊ ምርጫ የኢትዮጵያ ሀገረ-መንግሥታዊ ሥርዓት የሚጠነክርበትና የዴሞክራሲ ልምምድ አንድ ደረጃ ከፍ የሚልበት ወሳኝ አጋጣሚ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህንን የገለጹት ለ1447ኛው የዒድ አል አድሐ (ዐረፋ) በዓል ባስተላለፉት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት ላይ ነው።
የዐረፋ በዓል ማኅበረሰባዊ በዓል መሆኑን፣ ሰዎች በግላቸው ሳይሆን ከቤተሰብ፣ ጎረቤትና ማኅበረሰብ ጋር በመተሳሰብና በመተጋገዝ የሚያከብሩት መሆኑን ያወሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ ይህ ማኅበራዊ ትስስር ለዜጎችና ለሀገር ደኅንነት ወሳኝ መሆኑን አስምረውበታል።
ከዚሁ ማኅበራዊ ኃላፊነት ጋር በማያያዝም ምርጫን ዋነኛው የማኅበራዊና ዜግነታዊ ግዴታ መወጫ መሣሪያ አድርገው አቅርበውታል።
"ያለ ሕዝብ ተሳትፎ ዴሞክራሲ አይሳካም። ያለ ምርጫም የሕዝብ ተሳትፎ ምሉዕ አይሆንም" ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ፣ መጪው ምርጫ ብዝሃ-ድምፅ የሚሰማበትና የሕግ መወሰኛ ምክር ቤት የሚመሰረትበት ወሳኝ የታሪክ ምዕራፍ መሆኑን አብራርተዋል።
በመሆኑም መላው ሕዝበ ሙስሊም በዓሉን ሲያከብር ማኅበራዊ ግዴታውን በመወጣት ብቻ ሳይወሰን፣ በመጪው ምርጫ በድምፅ መስጫ ካርዱ ዴሞክራሲያዊ መብቱን ለማረጋገጥ ዝግጅት እንዲያደርግ ሀገራዊ ጥሪያቸውን አቅርበዋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #pmabiyahmed #democracy #ethiopianelection #civicduty #ethiopianbroadcastingcorporation
#ethiopia | የዘንድሮው ሀገራዊ ምርጫ የኢትዮጵያ ሀገረ-መንግሥታዊ ሥርዓት የሚጠነክርበትና የዴሞክራሲ ልምምድ አንድ ደረጃ ከፍ የሚልበት ወሳኝ አጋጣሚ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህንን የገለጹት ለ1447ኛው የዒድ አል አድሐ (ዐረፋ) በዓል ባስተላለፉት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት ላይ ነው።
የዐረፋ በዓል ማኅበረሰባዊ በዓል መሆኑን፣ ሰዎች በግላቸው ሳይሆን ከቤተሰብ፣ ጎረቤትና ማኅበረሰብ ጋር በመተሳሰብና በመተጋገዝ የሚያከብሩት መሆኑን ያወሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ ይህ ማኅበራዊ ትስስር ለዜጎችና ለሀገር ደኅንነት ወሳኝ መሆኑን አስምረውበታል።
ከዚሁ ማኅበራዊ ኃላፊነት ጋር በማያያዝም ምርጫን ዋነኛው የማኅበራዊና ዜግነታዊ ግዴታ መወጫ መሣሪያ አድርገው አቅርበውታል።
"ያለ ሕዝብ ተሳትፎ ዴሞክራሲ አይሳካም። ያለ ምርጫም የሕዝብ ተሳትፎ ምሉዕ አይሆንም" ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ፣ መጪው ምርጫ ብዝሃ-ድምፅ የሚሰማበትና የሕግ መወሰኛ ምክር ቤት የሚመሰረትበት ወሳኝ የታሪክ ምዕራፍ መሆኑን አብራርተዋል።
በመሆኑም መላው ሕዝበ ሙስሊም በዓሉን ሲያከብር ማኅበራዊ ግዴታውን በመወጣት ብቻ ሳይወሰን፣ በመጪው ምርጫ በድምፅ መስጫ ካርዱ ዴሞክራሲያዊ መብቱን ለማረጋገጥ ዝግጅት እንዲያደርግ ሀገራዊ ጥሪያቸውን አቅርበዋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #pmabiyahmed #democracy #ethiopianelection #civicduty #ethiopianbroadcastingcorporation
11 days ago
የሕልውና ማኅተም እና የትውልድ ጥሪ
*****************
ጥንታዊት እና ገናና ሀገር ኢትዮጵያ በታሪኳ ማህደር በርካታ የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚ እና የሥርዓት ሽግግሮችን አስተናግዳለች።
በዘውዱ ሥርዓት፣ ጠንካራ ማዕከላዊነትን፤ በደርግ ወታደራዊ ሶሻሊዝም የ17 ዓመታት ደም አፋሳሽ የእርስ በርስ ግጭትን እንዲሁም ከዚያ በኋላ በነበሩት ሦስት አሥርት ዓመታት ተፎካካሪዎችን በጠላትነት በሚመለከት አግላይ ትርክት የታጠረ የልማታዊ መንግሥት አውራ ፓርቲ ሥርዓትን አሳልፋለች።
እነዚህ መዋቅራዊ ስብራቶች ዛሬም ድረስ ከብርቱ ቁጭት ጋር ትልቅ ትምህርት ጥለውልን አልፈዋል።
አሁን የተጀመረው ሀገረ መንግሥቱን በጽኑ እና በማይናወጥ መሠረት ላይ የመገንባት ሂደት እንዲጠናከር 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ታሪካዊ እና ወሳኝ የሽግግር ምዕራፍ ነው።
ዴሞክራሲዋን በማዳበር ሂደት ላይ ያለችው ኢትዮጵያ፣ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ታካሂዳለች።
ይህ ምርጫ ተራ የድምፅ አሰጣጥ ሥነ-ሥርዓት ብቻ አይደለም። ይልቁንም የኢትዮጵያን ብሔራዊ አንድነት የማፅናት፣ የሕግ የበላይነትን የማስከበር እና የዜግነት ክብርን በዓለም ፊት ከፍ የማድረጊያ ታላቅ ብሔራዊ መድረክ ነው።
የዚህ ታሪካዊ ምርጫ የመጀመሪያውና ደማቁ ስኬት የተመዘገበው በሕዝባችን ነቂስ ተሳትፎ እና ታይቶ በማይታወቅ የመራጮች ምዝገባ ሂደት ነው።
በብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ይፋ በተደረገው መረጃ መሠረት፣ በአጠቃላይ ከ50.5 ሚሊዮን በላይ ዜጎች ለመራጭነት ተመዝግበዋል።
ይህ አስደናቂ እና ታሪካዊ ቁጥር ሕዝባችን የድምፅ መስጫ ሳጥንን ብቸኛው ሰላማዊ የለውጥ እና የጋራ ሀገር ግንባታ መሣሪያ አድርጎ በሙሉ ልብ መቀበሉን ያረጋግጣል።
ይህን ያህል ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ዜጎች ከግጭት እና ብጥብጥ ይልቅ በዴሞክራሲያዊ መንገድ ሥልጣንን ማሸጋገር የተሻለ እና ብቸኛ አማራጭ መሆኑን በማመን የምርጫ ካርዳቸውን መያዛቸው ሀገራችን ለደረሰችበት የፖለቲካ ብስለት ትልቅ ማሳያ ነው።
ይህ ሰፊ ሕዝባዊ ተሳትፎ የምርጫውን ተዓማኒነት እና ሕጋዊነት ከፍ የሚያደርገው ሲሆን፣ የሚመሠረተውን የሕዝብ ውክልና ይበልጥ ጽኑና ፍትሐዊ ያደርገዋል።
ከሁሉም በላይ፣ ይህ ምርጫ በተጨባጭ እየተካሄደ ያለው የተጀመረውን የሀገረ መንግሥት ግንባታ ሂደት በከፍተኛ ፍጥነት ለማሳለጥ እና ለማጠናከር ነው።
እውነተኛ የሀገረ መንግሥት ግንባታ የሚረጋገጠው ተቋማት ሕዝባዊ ይሁንታን ሲጎናጸፉ እና ማዕከላዊው መዋቅር ሰላምን ሲያሰፍን ነው።
በምርጫው የሚሰጠው እያንዳንዱ ድምፅ የሀገራችንን መዋቅራዊ ጽናት በማጠናከር በኩል እንደ ሕልውና ማኅተም ያገለግላል።
የተጀመሩ የኢኮኖሚ ማሻሻያዎችን በጽናት ለመምራት፣ የዜጎችን ማኅበራዊ ውል ለማደስ እና የሀገርን ሉዓላዊነት ለማስከበር የሚያግዝ የዜጎች ውል ነው።
ስለሆነም ሀገራችን በጥልቅ ስትራቴጂያዊ ዕቅድ ከጀመረቻቸው የብሔራዊ ምክክር እና የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲዎች ጋር በተቀናጀ መልኩ፣ ይህ ምርጫ ብሔራዊ መግባባትን የመፍጠሪያ እና ያለፉ የታሪክ ቁርሾዎችን በዘላቂነት የመፈወሻ ትልቁ መሣሪያ መሆን አለበት።
የምርጫው ውጤት ሕዝባዊ ውክልናን ምሉዕ በማድረግ፣ በጠረጴዛ ዙሪያ ለሚደረጉ ሀገራዊ ምክክሮች እውነተኛ የሕግና የሞራል መሠረት ይጥላል።
ከአንድ ሳምንት በኋላ የሚካሄደው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የሁላችንም የጋራ የቤት ሥራ እና የታሪክ አደራ ነው።
የኢትዮጵያ ሀገረ መንግሥት ዘላቂ ፅናት የሚረጋገጠው የምርጫ ጣቢያዎችን ሰላም በጋራ ስንጠብቅ፣ ተስፋ ከመቁረጥ እና ከዳር ተመልካችነት ወጥተን የዜግነት ድርሻችንን ስንወጣና እያንዳንዱ መራጭ በነፃነትና በደኅንነት ድምፁን ሲሰጥ ብቻ ነው።
ያለ ሰላም እና ማኅበራዊ መግባባት የሚደረግ ምርጫ ሙሉ ትርጉም ሊኖረው እንደማይችል አስቀድመን ተገንዝበን መንግሥት፣ ተፎካካሪ ፓርቲዎች፣ ሲቪክ ማኅበራት እና መላው ሕዝብ ሁላችንም ለሂደቱ ፍትሐዊነት፣ ግልጽነት እና ሰላማዊነት ዘብ መቆም አለብን።
ኑ! የታሪክ ስብራታችንን በጠረጴዛ ዙሪያ ውይይት እና በድምፅ መስጫ ሳጥን እንጠግን! በእያንዳንዱ ዜጋ ልቦና ውስጥ እውነተኛ የእኩልነት፣ የሰላም እና የፍትሕ ተስፋን እንዝራ።
ለሀገራችን መፅናት እና ለዴሞክራሲያችን ማብብ፣ የሀገረ መንግሥታችንን ምሰሶዎች ይበልጥ ለማጠንከር ሁላችንም በጋራ እንረባረብ።
ይህ ምርጫ ታሪካዊ ክብር እና የትውልድ ጥሪ ነው!
በአዶኒያስ ወልደአረጋይ
#ethiopia #politics #democracy #ebc
*****************
ጥንታዊት እና ገናና ሀገር ኢትዮጵያ በታሪኳ ማህደር በርካታ የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚ እና የሥርዓት ሽግግሮችን አስተናግዳለች።
በዘውዱ ሥርዓት፣ ጠንካራ ማዕከላዊነትን፤ በደርግ ወታደራዊ ሶሻሊዝም የ17 ዓመታት ደም አፋሳሽ የእርስ በርስ ግጭትን እንዲሁም ከዚያ በኋላ በነበሩት ሦስት አሥርት ዓመታት ተፎካካሪዎችን በጠላትነት በሚመለከት አግላይ ትርክት የታጠረ የልማታዊ መንግሥት አውራ ፓርቲ ሥርዓትን አሳልፋለች።
እነዚህ መዋቅራዊ ስብራቶች ዛሬም ድረስ ከብርቱ ቁጭት ጋር ትልቅ ትምህርት ጥለውልን አልፈዋል።
አሁን የተጀመረው ሀገረ መንግሥቱን በጽኑ እና በማይናወጥ መሠረት ላይ የመገንባት ሂደት እንዲጠናከር 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ታሪካዊ እና ወሳኝ የሽግግር ምዕራፍ ነው።
ዴሞክራሲዋን በማዳበር ሂደት ላይ ያለችው ኢትዮጵያ፣ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ታካሂዳለች።
ይህ ምርጫ ተራ የድምፅ አሰጣጥ ሥነ-ሥርዓት ብቻ አይደለም። ይልቁንም የኢትዮጵያን ብሔራዊ አንድነት የማፅናት፣ የሕግ የበላይነትን የማስከበር እና የዜግነት ክብርን በዓለም ፊት ከፍ የማድረጊያ ታላቅ ብሔራዊ መድረክ ነው።
የዚህ ታሪካዊ ምርጫ የመጀመሪያውና ደማቁ ስኬት የተመዘገበው በሕዝባችን ነቂስ ተሳትፎ እና ታይቶ በማይታወቅ የመራጮች ምዝገባ ሂደት ነው።
በብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ይፋ በተደረገው መረጃ መሠረት፣ በአጠቃላይ ከ50.5 ሚሊዮን በላይ ዜጎች ለመራጭነት ተመዝግበዋል።
ይህ አስደናቂ እና ታሪካዊ ቁጥር ሕዝባችን የድምፅ መስጫ ሳጥንን ብቸኛው ሰላማዊ የለውጥ እና የጋራ ሀገር ግንባታ መሣሪያ አድርጎ በሙሉ ልብ መቀበሉን ያረጋግጣል።
ይህን ያህል ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ዜጎች ከግጭት እና ብጥብጥ ይልቅ በዴሞክራሲያዊ መንገድ ሥልጣንን ማሸጋገር የተሻለ እና ብቸኛ አማራጭ መሆኑን በማመን የምርጫ ካርዳቸውን መያዛቸው ሀገራችን ለደረሰችበት የፖለቲካ ብስለት ትልቅ ማሳያ ነው።
ይህ ሰፊ ሕዝባዊ ተሳትፎ የምርጫውን ተዓማኒነት እና ሕጋዊነት ከፍ የሚያደርገው ሲሆን፣ የሚመሠረተውን የሕዝብ ውክልና ይበልጥ ጽኑና ፍትሐዊ ያደርገዋል።
ከሁሉም በላይ፣ ይህ ምርጫ በተጨባጭ እየተካሄደ ያለው የተጀመረውን የሀገረ መንግሥት ግንባታ ሂደት በከፍተኛ ፍጥነት ለማሳለጥ እና ለማጠናከር ነው።
እውነተኛ የሀገረ መንግሥት ግንባታ የሚረጋገጠው ተቋማት ሕዝባዊ ይሁንታን ሲጎናጸፉ እና ማዕከላዊው መዋቅር ሰላምን ሲያሰፍን ነው።
በምርጫው የሚሰጠው እያንዳንዱ ድምፅ የሀገራችንን መዋቅራዊ ጽናት በማጠናከር በኩል እንደ ሕልውና ማኅተም ያገለግላል።
የተጀመሩ የኢኮኖሚ ማሻሻያዎችን በጽናት ለመምራት፣ የዜጎችን ማኅበራዊ ውል ለማደስ እና የሀገርን ሉዓላዊነት ለማስከበር የሚያግዝ የዜጎች ውል ነው።
ስለሆነም ሀገራችን በጥልቅ ስትራቴጂያዊ ዕቅድ ከጀመረቻቸው የብሔራዊ ምክክር እና የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲዎች ጋር በተቀናጀ መልኩ፣ ይህ ምርጫ ብሔራዊ መግባባትን የመፍጠሪያ እና ያለፉ የታሪክ ቁርሾዎችን በዘላቂነት የመፈወሻ ትልቁ መሣሪያ መሆን አለበት።
የምርጫው ውጤት ሕዝባዊ ውክልናን ምሉዕ በማድረግ፣ በጠረጴዛ ዙሪያ ለሚደረጉ ሀገራዊ ምክክሮች እውነተኛ የሕግና የሞራል መሠረት ይጥላል።
ከአንድ ሳምንት በኋላ የሚካሄደው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የሁላችንም የጋራ የቤት ሥራ እና የታሪክ አደራ ነው።
የኢትዮጵያ ሀገረ መንግሥት ዘላቂ ፅናት የሚረጋገጠው የምርጫ ጣቢያዎችን ሰላም በጋራ ስንጠብቅ፣ ተስፋ ከመቁረጥ እና ከዳር ተመልካችነት ወጥተን የዜግነት ድርሻችንን ስንወጣና እያንዳንዱ መራጭ በነፃነትና በደኅንነት ድምፁን ሲሰጥ ብቻ ነው።
ያለ ሰላም እና ማኅበራዊ መግባባት የሚደረግ ምርጫ ሙሉ ትርጉም ሊኖረው እንደማይችል አስቀድመን ተገንዝበን መንግሥት፣ ተፎካካሪ ፓርቲዎች፣ ሲቪክ ማኅበራት እና መላው ሕዝብ ሁላችንም ለሂደቱ ፍትሐዊነት፣ ግልጽነት እና ሰላማዊነት ዘብ መቆም አለብን።
ኑ! የታሪክ ስብራታችንን በጠረጴዛ ዙሪያ ውይይት እና በድምፅ መስጫ ሳጥን እንጠግን! በእያንዳንዱ ዜጋ ልቦና ውስጥ እውነተኛ የእኩልነት፣ የሰላም እና የፍትሕ ተስፋን እንዝራ።
ለሀገራችን መፅናት እና ለዴሞክራሲያችን ማብብ፣ የሀገረ መንግሥታችንን ምሰሶዎች ይበልጥ ለማጠንከር ሁላችንም በጋራ እንረባረብ።
ይህ ምርጫ ታሪካዊ ክብር እና የትውልድ ጥሪ ነው!
በአዶኒያስ ወልደአረጋይ
#ethiopia #politics #democracy #ebc
15 days ago
ብልጽግና ፓርቲ በአማራ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች የምረጡኝ ቅስቀሳ አካሄደ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 13፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ብልጽግና ፓርቲ በአማራ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች የምረጡኝ ቅስቀሳ መርሐ ግብር አካሂዷል።
የፓርቲው የምርጡኝ ቅስቀሳ መርሐ ግብር “በጸና እና በተደራጀ የሴቶች ድምጽ ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገር እናሻግራለን” በሚል መሪ ሃሳብ ነው የተካሄደው፡፡
የምረጡኝ ቅስቀሳው በደብረ ማርቆስ፣ ላሊበላ፣ ዱርቤቴ፣ ሸዋሮቢት፣ ደንበጫ፣ ደብረታቦር፣ ወረኢሉ፣ አዴት፣ ደብረሲና፣ ወረታ፣ አጣዬ፣ ግንደወይን እና ሌሎች ከተሞች መከናወኑ ተመልክቷል፡፡
በምርጡኝ ቅስቀሳ መርሐ ግብሩ ላይ በየአካባቢዎቹ የሚገኙ የብልጽግና ፓርቲ የሴቶች ክንፍ አባላት እና ደጋፊዎች እንዲሁም ነዋሪዎች ተሳትፈዋል፡፡
በዚህ ወቅትም ብልጽግና ፓርቲ የሴቶችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ይበልጥ ለማሳደግ የሚሠራ ሀገራዊ ፓርቲ መሆኑን የሚያንጸባርቁ መልዕክቶች ተላልፈዋል፡፡
ተሳታፊዎቹ ለብልጽግና ፓርቲ ያላቸውን ጽኑ አጋርነት በመግለጽ ÷ ፓርቲው የጀመራቸውን የልማት፣ የሰላምና የብልጽግና ሥራዎች አጠናክሮ እንዲቀጥል የበኩላቸውን ሚና ለመወጣት ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠዋል፡፡
ሕጋዊ እና የጸና ሀገረ መንግሥት ለመመስረት ሴቶች በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በንቃት መሳተፍ እንዳለባቸውም በመርሐ ግብሩ ላይ ተጠቁሟል፡፡
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 13፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ብልጽግና ፓርቲ በአማራ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች የምረጡኝ ቅስቀሳ መርሐ ግብር አካሂዷል።
የፓርቲው የምርጡኝ ቅስቀሳ መርሐ ግብር “በጸና እና በተደራጀ የሴቶች ድምጽ ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገር እናሻግራለን” በሚል መሪ ሃሳብ ነው የተካሄደው፡፡
የምረጡኝ ቅስቀሳው በደብረ ማርቆስ፣ ላሊበላ፣ ዱርቤቴ፣ ሸዋሮቢት፣ ደንበጫ፣ ደብረታቦር፣ ወረኢሉ፣ አዴት፣ ደብረሲና፣ ወረታ፣ አጣዬ፣ ግንደወይን እና ሌሎች ከተሞች መከናወኑ ተመልክቷል፡፡
በምርጡኝ ቅስቀሳ መርሐ ግብሩ ላይ በየአካባቢዎቹ የሚገኙ የብልጽግና ፓርቲ የሴቶች ክንፍ አባላት እና ደጋፊዎች እንዲሁም ነዋሪዎች ተሳትፈዋል፡፡
በዚህ ወቅትም ብልጽግና ፓርቲ የሴቶችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ይበልጥ ለማሳደግ የሚሠራ ሀገራዊ ፓርቲ መሆኑን የሚያንጸባርቁ መልዕክቶች ተላልፈዋል፡፡
ተሳታፊዎቹ ለብልጽግና ፓርቲ ያላቸውን ጽኑ አጋርነት በመግለጽ ÷ ፓርቲው የጀመራቸውን የልማት፣ የሰላምና የብልጽግና ሥራዎች አጠናክሮ እንዲቀጥል የበኩላቸውን ሚና ለመወጣት ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠዋል፡፡
ሕጋዊ እና የጸና ሀገረ መንግሥት ለመመስረት ሴቶች በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በንቃት መሳተፍ እንዳለባቸውም በመርሐ ግብሩ ላይ ተጠቁሟል፡፡
17 days ago
u12e8u1320u1245u120bu12ed u121au1292u1235u1275u1229 u121bu122du123d u1240u12ebu122a u12cdu1233u1294 | u12a2u1275u12ee u1218u120du1215u1245 | PM Abiy Ahmed | Term Limit | Ethiopian Politics
#u12a2u1275u12eeu1335u12eb #u12d0u1262u12ed_u12a0u1215u1218u12f5 #u12e8u1225u120du1323u1295_u1308u12f0u1265 #u12f2u121eu12adu122bu1232 #u1200u1308u1228_u1218u1295u130du1225u1275 #u1270u124bu121bu1275 #u12a2u1275u12ee_u1218u120du1205u1245 #pmabiyahmed #termlimit #ethiopianpolitics #democracy #institutionalbuilding #ebcworld ","delight_ranges":[],"image_ranges":[],"inline_style_ranges":[],"aggregated_ranges":[],"ranges":[{"entity":{"__typename":"Hashtag","__isEntity":"Hashtag","url":"https://www.facebook.com/h...
የጠቅላይ ሚኒስትሩ ማርሽ ቀያሪ ውሳኔ | ኢትዮ መልሕቅ | PM Abiy Ahmed | Term Limit | Ethiopian Politics
#ኢትዮጵያ #ዐቢይ_አሕመድ #የሥልጣን_ገደብ #ዲሞክራሲ #ሀገረ_መንግሥት #ተቋማት #ኢትዮ_መልህቅ #pmabiyahmed #termlimit #ethiopianpolitics #democracy #institutionalbuilding #ebcworld
18 days ago
በዳታ ሉዓላዊነት ዙሪያ የተከናወኑ ስራዎች የዜጎችን ኑሮ ለማሻሻል ሊያገለግሉ ይገባል - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር)
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 10፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በዳታ ሉዓላዊነት ዙሪያ የተከናወኑ ስራዎች የዜጎችን የኑሮ ደረጃ ለመለወጥ ሊያገለግሉ ይገባል አሉ።
''የመረጃ ሉዓላዊነት ለፖሊሲ ነጻነት'' በሚል መሪ ሀሳብ ኢትዮጵያ በመረጃና በስታቲስቲክስ የሉዓላዊነት ጉዞ ባስመዘገበችው ስኬት ላይ ያተኮረ ሀገራዊ ጉባኤ ተካሂዷል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በመድረኩ ላይ፤ የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት በሳተላይት፣ በድሮንና በጂኦስፓሻል መረጃ የታገዘ ዘመናዊ አሰራርን መዘርጋቱ ለመላው ኢትዮጵያውያን ታላቅ ድል ነው ብለዋል።
በርካታ ሺህ ሰዎችን በማሰማራት የተሰበሰቡ መረጃዎችና ጥቅም ላይ የዋሉ ሳይንሳዊ ዘዴዎች ለሀገሪቱ ቀጣይ እድገትና ለሀገረ መንግሥት ግንባታ ጉልህ ሚና እንዳላቸው ጠቁመዋል።
በጥቂት ሀገራት ብቻ የሚታየውን የመረጃ አሰባሰብ፣ የትንተና እና የአቀራረብ ዘዴ በሀገር በቀል ባለሙያዎች ማየት መቻሉ ትልቅ የኩራት ምንጭ መሆኑንም ነው የገልጹት።
በመረጃ አሰባሰብ ሂደት ውስጥ በመስክ ላይ የሚሰበሰብ ተጨባጭ መረጃ የላቀ ዋጋ እንዳለው በማንሳት፤ የተሰበሰበው ዳታ በፖሊሲ ተደግፎና አመራር ተሰጥቶት ወደ ተጨባጭ ውጤት መሸጋገር ይገባዋል ነው ያሉት።
የተሰበሰበው ዳታ የመጨረሻ ግብ የእያንዳንዱን ሰው ህይወት መንካት፣ ማሻሻል እና ውጤት ማምጣት እንደሆነ ጠቅሰው፤ የሰው ህይወት መለወጡን ማረጋገጥ እንደሚገባ አመልክተዋል።
አርሶ አደሩ ከማምረት ባለፈ ልጆቹን ሲያስተምር፣ ህጻናት በምግብ እጥረት እንዳይጎዱ ሲደረግ እንዲሁም ይህንኑ እንደ ሀገራዊ ኢንቨስትመንት የሚገነዘቡ ዜጎች ሲበራከቱ መረጃው እውነተኛ ፋይዳውን አገኘ ማለት እንደሆነም አብራርተዋል።
በዮናስ ጌትነት
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 10፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በዳታ ሉዓላዊነት ዙሪያ የተከናወኑ ስራዎች የዜጎችን የኑሮ ደረጃ ለመለወጥ ሊያገለግሉ ይገባል አሉ።
''የመረጃ ሉዓላዊነት ለፖሊሲ ነጻነት'' በሚል መሪ ሀሳብ ኢትዮጵያ በመረጃና በስታቲስቲክስ የሉዓላዊነት ጉዞ ባስመዘገበችው ስኬት ላይ ያተኮረ ሀገራዊ ጉባኤ ተካሂዷል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በመድረኩ ላይ፤ የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት በሳተላይት፣ በድሮንና በጂኦስፓሻል መረጃ የታገዘ ዘመናዊ አሰራርን መዘርጋቱ ለመላው ኢትዮጵያውያን ታላቅ ድል ነው ብለዋል።
በርካታ ሺህ ሰዎችን በማሰማራት የተሰበሰቡ መረጃዎችና ጥቅም ላይ የዋሉ ሳይንሳዊ ዘዴዎች ለሀገሪቱ ቀጣይ እድገትና ለሀገረ መንግሥት ግንባታ ጉልህ ሚና እንዳላቸው ጠቁመዋል።
በጥቂት ሀገራት ብቻ የሚታየውን የመረጃ አሰባሰብ፣ የትንተና እና የአቀራረብ ዘዴ በሀገር በቀል ባለሙያዎች ማየት መቻሉ ትልቅ የኩራት ምንጭ መሆኑንም ነው የገልጹት።
በመረጃ አሰባሰብ ሂደት ውስጥ በመስክ ላይ የሚሰበሰብ ተጨባጭ መረጃ የላቀ ዋጋ እንዳለው በማንሳት፤ የተሰበሰበው ዳታ በፖሊሲ ተደግፎና አመራር ተሰጥቶት ወደ ተጨባጭ ውጤት መሸጋገር ይገባዋል ነው ያሉት።
የተሰበሰበው ዳታ የመጨረሻ ግብ የእያንዳንዱን ሰው ህይወት መንካት፣ ማሻሻል እና ውጤት ማምጣት እንደሆነ ጠቅሰው፤ የሰው ህይወት መለወጡን ማረጋገጥ እንደሚገባ አመልክተዋል።
አርሶ አደሩ ከማምረት ባለፈ ልጆቹን ሲያስተምር፣ ህጻናት በምግብ እጥረት እንዳይጎዱ ሲደረግ እንዲሁም ይህንኑ እንደ ሀገራዊ ኢንቨስትመንት የሚገነዘቡ ዜጎች ሲበራከቱ መረጃው እውነተኛ ፋይዳውን አገኘ ማለት እንደሆነም አብራርተዋል።
በዮናስ ጌትነት
18 days ago
መረጃ የዚህ ዘመን ስትራቴጂካዊ ሀብት እና ጠንካራ ሀገረ መንግሥት የሚገነባበት ቁልፍ የሉዓላዊነት ምሰሶ ነው፡- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
****************
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) "የመረጃ ሉዓላዊነት ለፖሊሲ ነጻነት" በሚል መሪ ሀሳብ በተካሄደው ሀገራዊ ጉባኤና ኤግዚቢሽን ላይ በመገኘት፣ ኢትዮጵያ በመረጃና በስታቲስቲክስ የሉዓላዊነት ጉዞ ያስመዘገበችውን ትልቅ ድል እና በዘርፉ የታየውን እመርታ ተመልክተው አድንቀዋል፡።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማኅበራዊ ትስስር ገጽ ባስተላፉት መልዕክት፤መረጃ የዚህ ዘመን ስትራቴጂካዊ ሀብት እና ጠንካራ ሀገረ መንግሥት የሚገነባበት ቁልፍ የሉዓላዊነት ምሰሶ ነው ሲሉ ገልጸዋል።
የተዋሰ አሊያም በውጭ አካላት ላይ ጥገኛ የሆነ መረጃ ሀገራዊ መሻትን ማሳካት ስለማያስችል የፖሊሲ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ የራስን መረጃ በራስ አቅም መሰብሰብ እና መተንተን ወሳኝ ግብዓት እንደሆነ አስገንዝበዋል።
አክለውም የመረጃ አሰባሰብና ትንተና ሥራው በሀገር ልጆች እውቀትና ክህሎት ሲከወን ማየት ታላቅ ሀገራዊ ኩራት መሆኑን የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ፣ ወደፊትም የመረጃ ትኩረታችን በቁጥር በሚገለጹ ውጤቶች ላይ ብቻ ሳይሆን ሰው ተኮር በሆኑና በዜጎች ሕይወት በሚታዩ ተጨባጭ ለውጦች ላይ ሊሆን እንደሚገባ አሳስበዋል።
#datasovereignty #policyindependence #ethiopia #pmabiyahmed #ethiopianbroadcastingcorporation
****************
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) "የመረጃ ሉዓላዊነት ለፖሊሲ ነጻነት" በሚል መሪ ሀሳብ በተካሄደው ሀገራዊ ጉባኤና ኤግዚቢሽን ላይ በመገኘት፣ ኢትዮጵያ በመረጃና በስታቲስቲክስ የሉዓላዊነት ጉዞ ያስመዘገበችውን ትልቅ ድል እና በዘርፉ የታየውን እመርታ ተመልክተው አድንቀዋል፡።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማኅበራዊ ትስስር ገጽ ባስተላፉት መልዕክት፤መረጃ የዚህ ዘመን ስትራቴጂካዊ ሀብት እና ጠንካራ ሀገረ መንግሥት የሚገነባበት ቁልፍ የሉዓላዊነት ምሰሶ ነው ሲሉ ገልጸዋል።
የተዋሰ አሊያም በውጭ አካላት ላይ ጥገኛ የሆነ መረጃ ሀገራዊ መሻትን ማሳካት ስለማያስችል የፖሊሲ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ የራስን መረጃ በራስ አቅም መሰብሰብ እና መተንተን ወሳኝ ግብዓት እንደሆነ አስገንዝበዋል።
አክለውም የመረጃ አሰባሰብና ትንተና ሥራው በሀገር ልጆች እውቀትና ክህሎት ሲከወን ማየት ታላቅ ሀገራዊ ኩራት መሆኑን የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ፣ ወደፊትም የመረጃ ትኩረታችን በቁጥር በሚገለጹ ውጤቶች ላይ ብቻ ሳይሆን ሰው ተኮር በሆኑና በዜጎች ሕይወት በሚታዩ ተጨባጭ ለውጦች ላይ ሊሆን እንደሚገባ አሳስበዋል።
#datasovereignty #policyindependence #ethiopia #pmabiyahmed #ethiopianbroadcastingcorporation
Sponsored by
Surafel
18 days ago
የውስጥ አንድነት - የባዕዳንን ሴራ መስበሪያ መሣሪያ
*****************
(የዕለቱ መልዕክት)
የአንድ ሀገር ሕልውና እና የሕዝቦች ሁለንተናዊ ብልጽግና መሠረቱ የማይናወጥ ዘላቂ ሰላም ነው። አባቶቻችን “ሰላም ለቤት፣ ፍቅር ለጎረቤት” የሚሉት በምክንያት ነው፤ ሰላም ልማት የሚፋጠንበት እና ጠንካራ ሀገረ-መንግሥት የሚገነባበት የሕልውናችን መሠረት ነውና።
ሰላም ሲጠፋ ግን የሀገር መረጋጋት ይናጋል፣ የቆሙበት ምድርም ይንሸራተታል። ባለፉት ዘመናት የታሪክ ትርክቶቻችን ወጥ የሆነ ሀገራዊ መግባባት ከመፍጠር ይልቅ፣ አንዱን ወገን ባለቤት ሌላውን ደግሞ ባዕድ የሚያደርጉ ፅንፈኛ አመለካከቶች መፈልፈያ ሆነው ቆይተዋል። ይህም የጋራ ማንነትን ከመገንባት ይልቅ ቅራኔን እና ቂምን በማስቀደም፣ ለውስጣዊ ግጭቶች መባባስ ማገዶ ሆኖ አገልግሏል።
“አጥር ሲፈርስ አውሬ ይገባል” እንዲሉ በተለይም ጠንካራ እና ገለልተኛ ተቋማት ያልነበሩ መሆኑ፣ የፖለቲካ ልዩነቶችን በሰላማዊ መንገድ ከመፍታት ይልቅ ወደ ግጭት እንዲያመሩ በማድረግ የሰላም እጦቱን ስር የሰደደ የታሪክ ጠባሳ አድርጎታል።
ከዚህ በተጨማሪ የኢትዮጵያ መልክዓ-ምድራዊ መገኛ ለሰላሟ መታወክ ሌላኛው ተጠቃሽ ምክንያት ነው። የቀይ ባሕር አቅራቢያ መሆኗ እና የዓባይ ወንዝ መገኛነቷ፣ ታሪካዊ ጠላቶች በውስጥ ጉዳያችን ላይ እጃቸውን እንዲያሰረዝሙ እና ምቀኝነት እንዲያሳድሩ በር ከፍቷል።
እነዚህ የውጭ ኃይሎች በውስጣችን ያሉ ጥቃቅን ልዩነቶችን በማጉላት ሀገራችን እንድትዳከም ሌት ተቀን ይሠራሉ። “ባንዳ ካልረዳ፣ የውጭ ጠላት አይጎዳ” እንደሚባለው ሁሉ፣ ይህ የባዕዳን ሴራ የሚፈጸመው ደግሞ የሀገርን ሕልውና ለግል እና ለቡድን ጥቅም ሲሉ አሳልፈው በሚሰጡ የሀገር ውስጥ ሆድ አደሮች አማካኝነት ነው።
እነዚህ ኃይሎች የታሪካዊ ጠላቶቻችንን እኩይ አጀንዳ ወደ ውስጥ በማስረግ እና ሕዝባዊ መከፋፈልን በመፍጠር፣ ሀገራችን በራሷ ዜጎች እንድትዳከም ሲያደርጉ ቆይተዋል፤ አሁንም ከዚህ የክህደት ተግባራቸው አልተቆጠቡም።
ይህንን የጥፋት እና የታሪክ አዙሪት ለመስበር እንዲሁም በሰላማዊ መንገድ የሚደረግ የፖለቲካ ውድድርን ለማስፈን የለውጡ መንግሥት ባለፉት ዓመታት ረጅም ርቀት ተጉዟል። ሀገርን ወደ ብልፅግና ለማሻገር የጸና ሰላም እና የቀና ሥርዓት ወሳኞች ናቸው። ስለሆነም ለሰላም ያለው ዕሳቤ ከመደበኛው “ጦርነት አለመኖር” ትርጓሜ የሰፋ እና ጥልቅ መሆን አለበት።
ይህ ዕሳቤ ሦስት ቁልፍ ምሰሶዎችን ያቀፈ ነው፤ አንደኛው ለግጭት መንሥኤ የሆኑ መዋቅራዊ ችግሮች ማለትም ድህነት፣ ኢ-ፍትሐዊነት እና መገለል የተቀረፉበት አዎንታዊ ሰላም መገንባት ሲሆን ሁለተኛው የኢትዮጵያ ሰላም ከጎረቤቶቿ ሰላም ጋር በእጅጉ የተቆራኘ መሆኑን በማመን ለቀጣናዊ ሰላም መከበር የመሪነት ሚና መጫወት ነው። ሦስተኛው እና ዋነኛው ደግሞ የአፍሪካ ችግር በአፍሪካውያን መፍትሔ በሚለው መርሕ መሠረት፣ ማንኛውንም ውስጣዊም ሆነ አህጉራዊ ግጭቶች በራሳችን ባህላዊ እና ዘመናዊ የሰላም እሴቶች፣ በሽምግልና እና በእርቅ መፍታት ነው።
ኢትዮጵያ ያለችበት ቀጣና ማዕበል የበዛበት እና ውስብስብ ቢሆንም፣ ሀገራችን ግን የሰላም ደሴት ሆና ሰላሟን በማጽናት ሁለንተናዊ ዕድገቷን እያሳለጠች እና የልማት ስበት ማዕከልነቷን እያጠናከረች ትገኛለች።
“ሰላምን ማስፈን ከራስ ይጀምራል” በሚል መርሕ በቀድሞው ሥርዓት በአሸባሪነት የተፈረጁ እና በሐሳብ ልዩነት ተሰስደው የነበሩ የፖለቲካ ኃይሎች ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ወደ ሀገር ውስጥ ገብተው ሰላማዊ እንቅስቃሴ እንዲያደርጉ ታሪካዊ ጥሪ ተደርጎላቸዋል፤ በአሁኑ ወቅትም በሰላማዊ መንገድ እየተንቀሳቀሱ ይገኛሉ።
ከዚህም በላይ ከጎረቤት ሀገራት ጋር በፈጠርነው የዲፕሎማሲ፣ የፀጥታ እና የኢኮኖሚ (የኤሌክትሪክ ኃይል፣ የመሠረተ ልማት እና የንግድ) ትሥሥር ምክንያት የእጅ አዙር ጥቃት ሥጋቶች፣ ሽብርተኝነት እና ድንበር ተሸጋሪ ወንጀሎች በከፍተኛ ሁኔታ እንዲገቱ ተደርጓል።
የመከላከያ እና የደኅንነት ተቋሞቻችንም ከፖለቲካ ወገንተኝነት የፀዱ፣ የሀገርን ዳር ድንበር ብቻ የሚጠብቁ እና ዘመናዊ ቴክኖሎጂ የታጠቁ ሆነው በታማኝነት ተገንብተዋል።
በአጠቃላይ አስተማማኝ ሰላምን ማረጋገጥ የሚቻለው የአሸናፊ እና ተሸናፊነትን፣ የቂም እና የቁርሾን ፖለቲካ ማክሰም ሲቻል ነው።
ታሪካዊ ቁስሎችን የምናክመውም በዕርቅ እና በሰላም መንገድ እንጂ በበቀል አይደለም፤ በቀል ማዕበልን እንጂ መረጋጋትን አይወልድምና።
ወደፊትም ሰላምን የሚያደፈርሱ ኃይላትን በሕግ ማስከበር መግታት ብቻ ሳይሆን ለግጭት ምክንያት የሆኑ አለመግባባቶችን በውይይት እና በንግግር ለመፍታት የተጀመሩ ሥራዎችን ዳር ማድረስ ያስፈልጋል።
እንደ ሀገር ሁለንተናዊ ብልጽግናችንን የሚያፀና ገዥ ትርክት ግንባታችንን አጠናክረን መቀጠል ይኖርብናል። ሰላምን፣ ትብብርን እና አብሮነትን ብቸኛ አማራጭ በማድረግ የምንከተለው የሰላም መንገድ ዛሬን ብቻ ሳይሆን ነገንም የሚያሻግር፣ ለልጆቻችን የምትመች እና የተከበረች ሀገር የምናስረክብበት ብቸኛው እና አስተማማኙ ጎዳና ነው።
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
#ebc #ethiopia #ebcdotstream #peace #narrative
*****************
(የዕለቱ መልዕክት)
የአንድ ሀገር ሕልውና እና የሕዝቦች ሁለንተናዊ ብልጽግና መሠረቱ የማይናወጥ ዘላቂ ሰላም ነው። አባቶቻችን “ሰላም ለቤት፣ ፍቅር ለጎረቤት” የሚሉት በምክንያት ነው፤ ሰላም ልማት የሚፋጠንበት እና ጠንካራ ሀገረ-መንግሥት የሚገነባበት የሕልውናችን መሠረት ነውና።
ሰላም ሲጠፋ ግን የሀገር መረጋጋት ይናጋል፣ የቆሙበት ምድርም ይንሸራተታል። ባለፉት ዘመናት የታሪክ ትርክቶቻችን ወጥ የሆነ ሀገራዊ መግባባት ከመፍጠር ይልቅ፣ አንዱን ወገን ባለቤት ሌላውን ደግሞ ባዕድ የሚያደርጉ ፅንፈኛ አመለካከቶች መፈልፈያ ሆነው ቆይተዋል። ይህም የጋራ ማንነትን ከመገንባት ይልቅ ቅራኔን እና ቂምን በማስቀደም፣ ለውስጣዊ ግጭቶች መባባስ ማገዶ ሆኖ አገልግሏል።
“አጥር ሲፈርስ አውሬ ይገባል” እንዲሉ በተለይም ጠንካራ እና ገለልተኛ ተቋማት ያልነበሩ መሆኑ፣ የፖለቲካ ልዩነቶችን በሰላማዊ መንገድ ከመፍታት ይልቅ ወደ ግጭት እንዲያመሩ በማድረግ የሰላም እጦቱን ስር የሰደደ የታሪክ ጠባሳ አድርጎታል።
ከዚህ በተጨማሪ የኢትዮጵያ መልክዓ-ምድራዊ መገኛ ለሰላሟ መታወክ ሌላኛው ተጠቃሽ ምክንያት ነው። የቀይ ባሕር አቅራቢያ መሆኗ እና የዓባይ ወንዝ መገኛነቷ፣ ታሪካዊ ጠላቶች በውስጥ ጉዳያችን ላይ እጃቸውን እንዲያሰረዝሙ እና ምቀኝነት እንዲያሳድሩ በር ከፍቷል።
እነዚህ የውጭ ኃይሎች በውስጣችን ያሉ ጥቃቅን ልዩነቶችን በማጉላት ሀገራችን እንድትዳከም ሌት ተቀን ይሠራሉ። “ባንዳ ካልረዳ፣ የውጭ ጠላት አይጎዳ” እንደሚባለው ሁሉ፣ ይህ የባዕዳን ሴራ የሚፈጸመው ደግሞ የሀገርን ሕልውና ለግል እና ለቡድን ጥቅም ሲሉ አሳልፈው በሚሰጡ የሀገር ውስጥ ሆድ አደሮች አማካኝነት ነው።
እነዚህ ኃይሎች የታሪካዊ ጠላቶቻችንን እኩይ አጀንዳ ወደ ውስጥ በማስረግ እና ሕዝባዊ መከፋፈልን በመፍጠር፣ ሀገራችን በራሷ ዜጎች እንድትዳከም ሲያደርጉ ቆይተዋል፤ አሁንም ከዚህ የክህደት ተግባራቸው አልተቆጠቡም።
ይህንን የጥፋት እና የታሪክ አዙሪት ለመስበር እንዲሁም በሰላማዊ መንገድ የሚደረግ የፖለቲካ ውድድርን ለማስፈን የለውጡ መንግሥት ባለፉት ዓመታት ረጅም ርቀት ተጉዟል። ሀገርን ወደ ብልፅግና ለማሻገር የጸና ሰላም እና የቀና ሥርዓት ወሳኞች ናቸው። ስለሆነም ለሰላም ያለው ዕሳቤ ከመደበኛው “ጦርነት አለመኖር” ትርጓሜ የሰፋ እና ጥልቅ መሆን አለበት።
ይህ ዕሳቤ ሦስት ቁልፍ ምሰሶዎችን ያቀፈ ነው፤ አንደኛው ለግጭት መንሥኤ የሆኑ መዋቅራዊ ችግሮች ማለትም ድህነት፣ ኢ-ፍትሐዊነት እና መገለል የተቀረፉበት አዎንታዊ ሰላም መገንባት ሲሆን ሁለተኛው የኢትዮጵያ ሰላም ከጎረቤቶቿ ሰላም ጋር በእጅጉ የተቆራኘ መሆኑን በማመን ለቀጣናዊ ሰላም መከበር የመሪነት ሚና መጫወት ነው። ሦስተኛው እና ዋነኛው ደግሞ የአፍሪካ ችግር በአፍሪካውያን መፍትሔ በሚለው መርሕ መሠረት፣ ማንኛውንም ውስጣዊም ሆነ አህጉራዊ ግጭቶች በራሳችን ባህላዊ እና ዘመናዊ የሰላም እሴቶች፣ በሽምግልና እና በእርቅ መፍታት ነው።
ኢትዮጵያ ያለችበት ቀጣና ማዕበል የበዛበት እና ውስብስብ ቢሆንም፣ ሀገራችን ግን የሰላም ደሴት ሆና ሰላሟን በማጽናት ሁለንተናዊ ዕድገቷን እያሳለጠች እና የልማት ስበት ማዕከልነቷን እያጠናከረች ትገኛለች።
“ሰላምን ማስፈን ከራስ ይጀምራል” በሚል መርሕ በቀድሞው ሥርዓት በአሸባሪነት የተፈረጁ እና በሐሳብ ልዩነት ተሰስደው የነበሩ የፖለቲካ ኃይሎች ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ወደ ሀገር ውስጥ ገብተው ሰላማዊ እንቅስቃሴ እንዲያደርጉ ታሪካዊ ጥሪ ተደርጎላቸዋል፤ በአሁኑ ወቅትም በሰላማዊ መንገድ እየተንቀሳቀሱ ይገኛሉ።
ከዚህም በላይ ከጎረቤት ሀገራት ጋር በፈጠርነው የዲፕሎማሲ፣ የፀጥታ እና የኢኮኖሚ (የኤሌክትሪክ ኃይል፣ የመሠረተ ልማት እና የንግድ) ትሥሥር ምክንያት የእጅ አዙር ጥቃት ሥጋቶች፣ ሽብርተኝነት እና ድንበር ተሸጋሪ ወንጀሎች በከፍተኛ ሁኔታ እንዲገቱ ተደርጓል።
የመከላከያ እና የደኅንነት ተቋሞቻችንም ከፖለቲካ ወገንተኝነት የፀዱ፣ የሀገርን ዳር ድንበር ብቻ የሚጠብቁ እና ዘመናዊ ቴክኖሎጂ የታጠቁ ሆነው በታማኝነት ተገንብተዋል።
በአጠቃላይ አስተማማኝ ሰላምን ማረጋገጥ የሚቻለው የአሸናፊ እና ተሸናፊነትን፣ የቂም እና የቁርሾን ፖለቲካ ማክሰም ሲቻል ነው።
ታሪካዊ ቁስሎችን የምናክመውም በዕርቅ እና በሰላም መንገድ እንጂ በበቀል አይደለም፤ በቀል ማዕበልን እንጂ መረጋጋትን አይወልድምና።
ወደፊትም ሰላምን የሚያደፈርሱ ኃይላትን በሕግ ማስከበር መግታት ብቻ ሳይሆን ለግጭት ምክንያት የሆኑ አለመግባባቶችን በውይይት እና በንግግር ለመፍታት የተጀመሩ ሥራዎችን ዳር ማድረስ ያስፈልጋል።
እንደ ሀገር ሁለንተናዊ ብልጽግናችንን የሚያፀና ገዥ ትርክት ግንባታችንን አጠናክረን መቀጠል ይኖርብናል። ሰላምን፣ ትብብርን እና አብሮነትን ብቸኛ አማራጭ በማድረግ የምንከተለው የሰላም መንገድ ዛሬን ብቻ ሳይሆን ነገንም የሚያሻግር፣ ለልጆቻችን የምትመች እና የተከበረች ሀገር የምናስረክብበት ብቸኛው እና አስተማማኙ ጎዳና ነው።
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
#ebc #ethiopia #ebcdotstream #peace #narrative
21 days ago
የኢትዮጵያ አዲሱ የቃል-ኪዳን ድልድይ፡ ከቂም በቀል ስብራት ወደ ምክክር መድኃኒት!
*********************
( የዕለቱ መልዕክት)
ቂምን አዝሎ መሮጥ መድረሻው ገደል ነው እንዲሉ ኢትዮጵያ ላለፉት ዘመናት በታሪካዊና መዋቅራዊ ስብራቶች ውስጥ የቆየችው ያለፈውን ቁስል በዝምታ ሸፍኖ፣ ነገን በጠመንጃ አፈሙዝ ለመቅረጽ በመሞከሯ ነው። ዛሬ ግን ይህንን የጥፋት አዙሪት የሚሰብር አዲስ የታሪክ ምዕራፍ ተከፍቷል።
መንግሥት እንደ ትልቅ የሰላም ምሰሶ የተጠቀመበት ትናንትን በሽግግር ፍትሕ የማረም፣ ነገን ደግሞ በሀገራዊ ምክክር የመገንባት" ስትራቴጂ፣ ሀገራችን ለዘመናት ስትጠብቀው የነበረው የሰላም ድልድይ ነው።
ያለፉ በደሎች እና ግጭቶች ሳይታረሙና ተገቢው ፍትሕ ሳይሰጥ ወደ ፊት ለመጓዝ መሞከር የቆሰለን እግር ሳይታከሙ ለሩጫ እንደመዘጋጀት ይቆጠራል።
የሽግግር ፍትሕ ያለፈውን ሸክም የሚያቀልል ሲሆን ሀገራዊ ምክክር ደግሞ የነገውን መንገድ የሚጠርግ በመሆኑ ሁለቱ ሂደቶች የማይነጣጠሉና ተመጋጋሚ የሰላም መሣሪያዎች ናቸው።
ኢትዮጵያ የበርካታ ማንነቶችና ጥንታዊ እሴቶች ባለቤት ብትሆንም፣ በታሪክ አጋጣሚ የተቀነቀኑ የበደል ትርክቶች ለሀገረ መንግሥት ግንባታው ትልቅ ፈተና ሆነው ቆይተዋል።
ይህንን ስብራት ለመጠገን የተወጠነው ሀገራዊ ምክክር ግን ልዩነቶች በጠረጴዛ ዙሪያ በሰለጠነ መንገድ እንዲፈቱ የሚያስችል ብቸኛው አማራጭ ነው። ምክክሩ፡፡ “ለካስ ስለ ሀገሬ እኔም መምከር እችላለሁ፤ ለካስ የእኔም ድምፅ ይሰማል” የሚሉ ዜጎች ወደ ምክክሩ ቀርበዋል።
ከወረዳ እስከ ፌደራል፣ ከሀገር ውስጥ እስከ ባህር ማዶ ያሉ ኢትዮጵያውያን በአንድነት ቁጭ ብለው በጋራ እንዲመክሩ መደረጉ፣ ሂደቱ ምን ያህል አካታችና ተዓማኒ እንደሆነ ማሳያ ነው። የተበታተኑ ሐሳቦች ወደ አንድ የጋራ አጀንዳ መምጣታቸው ለሀገራዊ መግባባት የጸና መሠረት ይጥላል።
ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን አጀንዳዎችን በማሰባሰብ ረገድ ያከናወናቸው ተግባራት ለዴሞክራሲ ሥርዓት መጎልበት ትልቅ ፋይዳ አላቸው። በቅርቡ በአማራ ክልል በትጥቅ ትግል ላይ የነበሩ ወገኖች ሰላምን መርጠው ወደ ምክክር መድረኩ መምጣታቸው፣ የሐሳብ የበላይነት ከጠመንጃ ኃይል እንደሚበልጥ በተግባር ያሳየ ስኬት ነው።
ዛሬ ላይ የምናደርገው ምክክር የነገዋን ኢትዮጵያ ዕጣ ፈንታ ይወስናል። የቂም ቁርሾን ለትናንት ትተን፣ በፍቅር እና በውይይት የምትመራ፣ ለልጆቻችን የምትመች እና በሁለንተናዊ ብልጽግና የደመቀች ኢትዮጵያን መገንባት የትውልዱ የቤት ሥራ ነው።
በዋና ዋና ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ የሚደረገው ታላቁ ጉባኤ ሲጀመር፣ እያንዳንዱ ዜጋ ሂደቱን በባለቤትነት ሊደግፈውና ሊሳተፍበት ይገባል።
የሀገራችንን ሰላም በጋራ ጥረት የምናጸናበት ወቅት ላይ እንገኛለን። ኢትዮጵያ ልዩነቶቿን በሰለጠነ ባህል የምትፈታ ሀገር እንድትሆን፣ ይህ ታሪካዊ የምክክር ጅማሮ ወደ ስኬት እንዲሻገር ሁላችንም የሰላም ጀግኖች ልንሆን ይገባል። ነገ ለልጆቻችን የምናወርሰው ሀገር በዛሬው ምክክራችንና በምናሳየው መቻቻል ላይ የተመሠረተ በመሆኑ ይህንን ወርቃማ ዕድል መጠቀም የታሪክ አደራ ነው።
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
*********************
( የዕለቱ መልዕክት)
ቂምን አዝሎ መሮጥ መድረሻው ገደል ነው እንዲሉ ኢትዮጵያ ላለፉት ዘመናት በታሪካዊና መዋቅራዊ ስብራቶች ውስጥ የቆየችው ያለፈውን ቁስል በዝምታ ሸፍኖ፣ ነገን በጠመንጃ አፈሙዝ ለመቅረጽ በመሞከሯ ነው። ዛሬ ግን ይህንን የጥፋት አዙሪት የሚሰብር አዲስ የታሪክ ምዕራፍ ተከፍቷል።
መንግሥት እንደ ትልቅ የሰላም ምሰሶ የተጠቀመበት ትናንትን በሽግግር ፍትሕ የማረም፣ ነገን ደግሞ በሀገራዊ ምክክር የመገንባት" ስትራቴጂ፣ ሀገራችን ለዘመናት ስትጠብቀው የነበረው የሰላም ድልድይ ነው።
ያለፉ በደሎች እና ግጭቶች ሳይታረሙና ተገቢው ፍትሕ ሳይሰጥ ወደ ፊት ለመጓዝ መሞከር የቆሰለን እግር ሳይታከሙ ለሩጫ እንደመዘጋጀት ይቆጠራል።
የሽግግር ፍትሕ ያለፈውን ሸክም የሚያቀልል ሲሆን ሀገራዊ ምክክር ደግሞ የነገውን መንገድ የሚጠርግ በመሆኑ ሁለቱ ሂደቶች የማይነጣጠሉና ተመጋጋሚ የሰላም መሣሪያዎች ናቸው።
ኢትዮጵያ የበርካታ ማንነቶችና ጥንታዊ እሴቶች ባለቤት ብትሆንም፣ በታሪክ አጋጣሚ የተቀነቀኑ የበደል ትርክቶች ለሀገረ መንግሥት ግንባታው ትልቅ ፈተና ሆነው ቆይተዋል።
ይህንን ስብራት ለመጠገን የተወጠነው ሀገራዊ ምክክር ግን ልዩነቶች በጠረጴዛ ዙሪያ በሰለጠነ መንገድ እንዲፈቱ የሚያስችል ብቸኛው አማራጭ ነው። ምክክሩ፡፡ “ለካስ ስለ ሀገሬ እኔም መምከር እችላለሁ፤ ለካስ የእኔም ድምፅ ይሰማል” የሚሉ ዜጎች ወደ ምክክሩ ቀርበዋል።
ከወረዳ እስከ ፌደራል፣ ከሀገር ውስጥ እስከ ባህር ማዶ ያሉ ኢትዮጵያውያን በአንድነት ቁጭ ብለው በጋራ እንዲመክሩ መደረጉ፣ ሂደቱ ምን ያህል አካታችና ተዓማኒ እንደሆነ ማሳያ ነው። የተበታተኑ ሐሳቦች ወደ አንድ የጋራ አጀንዳ መምጣታቸው ለሀገራዊ መግባባት የጸና መሠረት ይጥላል።
ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን አጀንዳዎችን በማሰባሰብ ረገድ ያከናወናቸው ተግባራት ለዴሞክራሲ ሥርዓት መጎልበት ትልቅ ፋይዳ አላቸው። በቅርቡ በአማራ ክልል በትጥቅ ትግል ላይ የነበሩ ወገኖች ሰላምን መርጠው ወደ ምክክር መድረኩ መምጣታቸው፣ የሐሳብ የበላይነት ከጠመንጃ ኃይል እንደሚበልጥ በተግባር ያሳየ ስኬት ነው።
ዛሬ ላይ የምናደርገው ምክክር የነገዋን ኢትዮጵያ ዕጣ ፈንታ ይወስናል። የቂም ቁርሾን ለትናንት ትተን፣ በፍቅር እና በውይይት የምትመራ፣ ለልጆቻችን የምትመች እና በሁለንተናዊ ብልጽግና የደመቀች ኢትዮጵያን መገንባት የትውልዱ የቤት ሥራ ነው።
በዋና ዋና ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ የሚደረገው ታላቁ ጉባኤ ሲጀመር፣ እያንዳንዱ ዜጋ ሂደቱን በባለቤትነት ሊደግፈውና ሊሳተፍበት ይገባል።
የሀገራችንን ሰላም በጋራ ጥረት የምናጸናበት ወቅት ላይ እንገኛለን። ኢትዮጵያ ልዩነቶቿን በሰለጠነ ባህል የምትፈታ ሀገር እንድትሆን፣ ይህ ታሪካዊ የምክክር ጅማሮ ወደ ስኬት እንዲሻገር ሁላችንም የሰላም ጀግኖች ልንሆን ይገባል። ነገ ለልጆቻችን የምናወርሰው ሀገር በዛሬው ምክክራችንና በምናሳየው መቻቻል ላይ የተመሠረተ በመሆኑ ይህንን ወርቃማ ዕድል መጠቀም የታሪክ አደራ ነው።
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
22 days ago
የተቋማት ግንባታ ለሀገር ልዕልና…
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 6፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) አንድ ሀገር ጠንካራ እና ተከታታይነት ያለውን ዕድገት ማስመዝገብ የሚችለው ጠንካራ ተቋማት ሲኖሩ እንደሆነ እሙን ነው።
በዚህም ተቋማት ለሀገረ መንግሥት ግንባታ ምሰሶ በመሆን የዜጎች እኩልና ፍትሃዊ ተጠቃሚነትን በማረጋገጥ ረገድ ጉልህ ሚና ይጫወታሉ።
በተለይም የፀጥታ እና የዴሞክራሲ ተቋማት ሪፎርም ለዚህ ትልቅ ሚና ያላቸው ሲሆን÷ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ወደ ስልጣን ከመጡ ወዲህ ለዘርፉ ትኩረት በመስጠት የሪፎርም ስራዎች ተከናውነዋል።
በዚሁም ኢትዮጵያ ታፍራ እና ተከብራ እንድትኖር የሚያስችል መሰረት መጣል ተችሏል።
ተቋማቱ በአመራርና በሰው ኃይል የተጠናከሩ፣ አቅማቸው በቴክኖሎጂ የበለፀገ፣ በደኅንነት መሰረታዊና አንኳር ክህሎቶች የፈረጠሙ እና በዴሞክራሲያዊ መሰረት ላይ የታነፁ ነፃ፣ ገለልተኛ እና ብቃት ያላቸው እንዲሆኑ ሰፊ ስራዎች ተከናውነዋል።
በውጤቱም ለሀገርና ለሕዝብ ጥቅም የቆሙ፣ ወገንተኝነታቸው ለህግ ብቻ የሆኑ፣ ጠላቶች ኢትዮጵያ ላይ ፈፅሞ ክፉ እንዳያስቡ የሚያደርጉ፣ ለሀገር ጋሻ እና ጥላ የሆኑ ተቋማት ተገንብተዋል።
በተከናወኑ የሪፎርም ስራዎች በዘርፉ የሚስተዋሉ ስጋቶችን ከመቀልበስ ባሻገር ቀድሞ ችግሮችን በመለየትና አዝማሚያዎችን በመተንተን ድንገተኛ የሚባሉ የደኅንነትና የፀጥታ ክፍተቶችን ማስቀረት እየተቻለም ይገኛል።
በተጨማሪም ከሀገራዊ ለውጡ ማግስት መከላከያ ሠራዊትን ጨምሮ በፀጥታና ደኅንነት ተቋማት በተደረገው ሪፎርም ውትድርና ጀግኖች የሚመርጡት ለሀገር ሉዓላዊ አንድነት ዋጋ የሚከፈልበት የተከበረ ሙያ መሆን ችሏል።
በዚህም ለኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ዘመናዊ ትጥቅን በማሟላት የሀገርን ተጋላጭነት ማስቀረት የሚችል አስተማማኝ ኃይል ማድረግ ተችሏል።
ለዚህም የሆሚቾ ጥይት ፋብሪካ እና የድሮን ቴክኖሎጂዎችን የሚያመርተው ስካይዊን ኤሮኖቲክስ ኢንዱስትሪ በመገንባት ስራ መጀመራቸው ተጠቃሽ ናቸው፡፡
እንዲሁም ኢትዮጵያ ከዘመኑ ጋር መጓዝ እንድትችል መንግሥት የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩትን በማቋቋም ለዘርፉ ከፍተኛ ትኩረት በመስጠት እየሰራ ይገኛል።
አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ አሁን በዓለም አቀፍ ደረጃ በፍጥነት እያደገ የሚገኝ ዘርፍ ሲሆን÷ የሰዎችን ህይወት ቀላል በማድረግ በተለያዩ ዘርፎች ለተለያዩ ዓለማ በመዋል ላይ ይገኛል።
ኢትዮጵያም የዘርፉን ሚና በመገንዘብ ተቋም በመገንባት "ኤአይ ለሁሉም" በሚል መሪ ሐሳብ የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ዩኒቨርሲቲ ለማቋቋም ከጫፍ ደርሳለች።
በተጨማሪም መንግሥት በጸጥታ አካላት፣ በሰብዓዊ መብት ተቋማት፣ በብሔራዊ ምርጫ ቦርድ፣ በፍትሕ አካላትና በሌሎች የዴሞክራሲ ተቋማት ላይ ሪፎርም ማድረጉ የሚታወስ ነው።
በአድማሱ አራጋው
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 6፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) አንድ ሀገር ጠንካራ እና ተከታታይነት ያለውን ዕድገት ማስመዝገብ የሚችለው ጠንካራ ተቋማት ሲኖሩ እንደሆነ እሙን ነው።
በዚህም ተቋማት ለሀገረ መንግሥት ግንባታ ምሰሶ በመሆን የዜጎች እኩልና ፍትሃዊ ተጠቃሚነትን በማረጋገጥ ረገድ ጉልህ ሚና ይጫወታሉ።
በተለይም የፀጥታ እና የዴሞክራሲ ተቋማት ሪፎርም ለዚህ ትልቅ ሚና ያላቸው ሲሆን÷ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ወደ ስልጣን ከመጡ ወዲህ ለዘርፉ ትኩረት በመስጠት የሪፎርም ስራዎች ተከናውነዋል።
በዚሁም ኢትዮጵያ ታፍራ እና ተከብራ እንድትኖር የሚያስችል መሰረት መጣል ተችሏል።
ተቋማቱ በአመራርና በሰው ኃይል የተጠናከሩ፣ አቅማቸው በቴክኖሎጂ የበለፀገ፣ በደኅንነት መሰረታዊና አንኳር ክህሎቶች የፈረጠሙ እና በዴሞክራሲያዊ መሰረት ላይ የታነፁ ነፃ፣ ገለልተኛ እና ብቃት ያላቸው እንዲሆኑ ሰፊ ስራዎች ተከናውነዋል።
በውጤቱም ለሀገርና ለሕዝብ ጥቅም የቆሙ፣ ወገንተኝነታቸው ለህግ ብቻ የሆኑ፣ ጠላቶች ኢትዮጵያ ላይ ፈፅሞ ክፉ እንዳያስቡ የሚያደርጉ፣ ለሀገር ጋሻ እና ጥላ የሆኑ ተቋማት ተገንብተዋል።
በተከናወኑ የሪፎርም ስራዎች በዘርፉ የሚስተዋሉ ስጋቶችን ከመቀልበስ ባሻገር ቀድሞ ችግሮችን በመለየትና አዝማሚያዎችን በመተንተን ድንገተኛ የሚባሉ የደኅንነትና የፀጥታ ክፍተቶችን ማስቀረት እየተቻለም ይገኛል።
በተጨማሪም ከሀገራዊ ለውጡ ማግስት መከላከያ ሠራዊትን ጨምሮ በፀጥታና ደኅንነት ተቋማት በተደረገው ሪፎርም ውትድርና ጀግኖች የሚመርጡት ለሀገር ሉዓላዊ አንድነት ዋጋ የሚከፈልበት የተከበረ ሙያ መሆን ችሏል።
በዚህም ለኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ዘመናዊ ትጥቅን በማሟላት የሀገርን ተጋላጭነት ማስቀረት የሚችል አስተማማኝ ኃይል ማድረግ ተችሏል።
ለዚህም የሆሚቾ ጥይት ፋብሪካ እና የድሮን ቴክኖሎጂዎችን የሚያመርተው ስካይዊን ኤሮኖቲክስ ኢንዱስትሪ በመገንባት ስራ መጀመራቸው ተጠቃሽ ናቸው፡፡
እንዲሁም ኢትዮጵያ ከዘመኑ ጋር መጓዝ እንድትችል መንግሥት የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩትን በማቋቋም ለዘርፉ ከፍተኛ ትኩረት በመስጠት እየሰራ ይገኛል።
አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ አሁን በዓለም አቀፍ ደረጃ በፍጥነት እያደገ የሚገኝ ዘርፍ ሲሆን÷ የሰዎችን ህይወት ቀላል በማድረግ በተለያዩ ዘርፎች ለተለያዩ ዓለማ በመዋል ላይ ይገኛል።
ኢትዮጵያም የዘርፉን ሚና በመገንዘብ ተቋም በመገንባት "ኤአይ ለሁሉም" በሚል መሪ ሐሳብ የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ዩኒቨርሲቲ ለማቋቋም ከጫፍ ደርሳለች።
በተጨማሪም መንግሥት በጸጥታ አካላት፣ በሰብዓዊ መብት ተቋማት፣ በብሔራዊ ምርጫ ቦርድ፣ በፍትሕ አካላትና በሌሎች የዴሞክራሲ ተቋማት ላይ ሪፎርም ማድረጉ የሚታወስ ነው።
በአድማሱ አራጋው
1 month ago
የኢትዮጵያ አየር መንገድ፦ የሀገረ መንግሥት ግንባታ ምሰሶና የአፍሪካ አቪየሽን የልህቀት ማማ
*****************
የኢትዮጵያ አየር መንገድ በሀገር ግንባታ ሂደት ካለው ጉልህ ሚና ባለፈ፣ ብሔራዊ ኩራትን በመፍጠር ረገድ የአፍሪካ አቪየሽን የልህቀት ተምሳሌት መሆኑን የመንግሥት ከፍተኛ አመራሮች ገለጹ።
አየር መንገዱ የተመሠረተበትን 80ኛ ዓመት ምክንያት በማድረግ፣ ከደንበኞችና ከአጋሮች ጋር የልምድ ልውውጥ የሚደረግበት "የደንበኞች ተሞክሮ መድረክ" እየተካሄደ ይገኛል።
በዚሁ መርሐ ግብር ላይ የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ፣ የፕላንና ልማት ሚኒስትሯ ፍጹም አሰፋ (ዶ/ር)፣ የገንዘብ ሚኒስትር ድኤታው ኢዮብ ተካልኝ (ዶ/ር) እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው የክብር እንግዶች ተገኝተዋል።
በዕለቱ በተካሄደው የፓናል ውይይት ላይ የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ እንደገለጹት፤ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የላቀ ውጤት ያስመዘገበና ለረጅም ዓመታት ስኬቱን ማስቀጠል የቻለ ግዙፍ የመንግሥት የንግድ ተቋም ነው።
አየር መንገዱ ለኢትዮጵያ ሀገረ መንግሥት ግንባታ እንዲሁም ለፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ ዕድገት ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ እንደሚገኝም አክለው ገልጸዋል።
በተለይም ኢትዮጵያ ከሌሎች ሀገራት ጋር ያላትን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነትና የሀገር ውስጥ ትስስርን ለማጠናከር ተቋሙ የማይተካ ሚና እንዳለው አስገንዝበዋል።
የፕላንና ልማት ሚኒስትሯ ፍጹም አሰፋ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ አየር መንገዱ የሀገር ኩራትና ሁሉም ዜጋ "የእኔ" የሚለው የጋራ ማንነት መገለጫ የሆነ ብሔራዊ ድርጅት መሆኑን ገልጸዋል።
ተቋሙ ለኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ለመላው አፍሪካ "የመቻል" እና የልህቀት ማሳያ መሆኑን ጠቅሰው፤ ይህም የሀገራችንን የማድረግ አቅም ለዓለም የሚያሳይ መሆኑን ተናግረዋል።
አየር መንገዱ ለአገልግሎት ዘርፍ ወጪ ንግድ (Export) ካለው ከፍተኛ ድርሻ በተጨማሪ፣ ለንግድ ሥርዓቱ መሳለጥና ለሥራ ዕድል ፈጠራ ትልቅ አቅም እየሆነ እንደሚገኝም አስረድተዋል።
የገንዘብ ሚኒስትር ድኤታው ኢዮብ ተካልኝ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ አየር መንገዱ ግዙፍ የሎጅስቲክስ መሠረተ ልማት አቅም መገንባቱን ገልጸው፤ ለወጪ ንግድና ለዲፕሎማሲ ስኬት ቁልፍ ሚና ያለው ተቋም መሆኑን እንደጠቆሙ የዘገበው ኢዜአ ነው።
#ethiopianairlines #flyethiopian #80yearsofexcellence #timelesslegacy #aviationhistory
*****************
የኢትዮጵያ አየር መንገድ በሀገር ግንባታ ሂደት ካለው ጉልህ ሚና ባለፈ፣ ብሔራዊ ኩራትን በመፍጠር ረገድ የአፍሪካ አቪየሽን የልህቀት ተምሳሌት መሆኑን የመንግሥት ከፍተኛ አመራሮች ገለጹ።
አየር መንገዱ የተመሠረተበትን 80ኛ ዓመት ምክንያት በማድረግ፣ ከደንበኞችና ከአጋሮች ጋር የልምድ ልውውጥ የሚደረግበት "የደንበኞች ተሞክሮ መድረክ" እየተካሄደ ይገኛል።
በዚሁ መርሐ ግብር ላይ የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ፣ የፕላንና ልማት ሚኒስትሯ ፍጹም አሰፋ (ዶ/ር)፣ የገንዘብ ሚኒስትር ድኤታው ኢዮብ ተካልኝ (ዶ/ር) እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው የክብር እንግዶች ተገኝተዋል።
በዕለቱ በተካሄደው የፓናል ውይይት ላይ የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ እንደገለጹት፤ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የላቀ ውጤት ያስመዘገበና ለረጅም ዓመታት ስኬቱን ማስቀጠል የቻለ ግዙፍ የመንግሥት የንግድ ተቋም ነው።
አየር መንገዱ ለኢትዮጵያ ሀገረ መንግሥት ግንባታ እንዲሁም ለፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ ዕድገት ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ እንደሚገኝም አክለው ገልጸዋል።
በተለይም ኢትዮጵያ ከሌሎች ሀገራት ጋር ያላትን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነትና የሀገር ውስጥ ትስስርን ለማጠናከር ተቋሙ የማይተካ ሚና እንዳለው አስገንዝበዋል።
የፕላንና ልማት ሚኒስትሯ ፍጹም አሰፋ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ አየር መንገዱ የሀገር ኩራትና ሁሉም ዜጋ "የእኔ" የሚለው የጋራ ማንነት መገለጫ የሆነ ብሔራዊ ድርጅት መሆኑን ገልጸዋል።
ተቋሙ ለኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ለመላው አፍሪካ "የመቻል" እና የልህቀት ማሳያ መሆኑን ጠቅሰው፤ ይህም የሀገራችንን የማድረግ አቅም ለዓለም የሚያሳይ መሆኑን ተናግረዋል።
አየር መንገዱ ለአገልግሎት ዘርፍ ወጪ ንግድ (Export) ካለው ከፍተኛ ድርሻ በተጨማሪ፣ ለንግድ ሥርዓቱ መሳለጥና ለሥራ ዕድል ፈጠራ ትልቅ አቅም እየሆነ እንደሚገኝም አስረድተዋል።
የገንዘብ ሚኒስትር ድኤታው ኢዮብ ተካልኝ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ አየር መንገዱ ግዙፍ የሎጅስቲክስ መሠረተ ልማት አቅም መገንባቱን ገልጸው፤ ለወጪ ንግድና ለዲፕሎማሲ ስኬት ቁልፍ ሚና ያለው ተቋም መሆኑን እንደጠቆሙ የዘገበው ኢዜአ ነው።
#ethiopianairlines #flyethiopian #80yearsofexcellence #timelesslegacy #aviationhistory
Sponsored by
Surafel
3 months ago
"ምክክር እውነት ፍለጋ መንገድ ነው!"
— ዶ/ር ዮናስ አዳዬ
#ethiopia | በሀገራችን ዘላቂ ሰላም ለመገንባትና ጠንካራ ሀገረ መንግሥት ለመመሥረት ከመመካከር ውጭ አማራጭ እንደሌለ የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ኮሚሽነር ዶ/ር ዮናስ አዳዬ በድጋሚ አስገንዝበዋል።
ዛሬ በአዳማ ከተማ ከሚዲያ ተቋማት ጋር ምክክር እያደረገ ይገኛል።
የምክክሩ ዋና ዓላማዎችና ፋይዳዎች፦
* እውነትን ማፈላለግ፦
ያለፉ ስህተቶችን በቅንነት በመፈተሽ፣ እውነተኛ ታሪክን በመረዳትና መፍትሔዎችን በማመንጨት የጋራ "እውነት" ላይ መድረስ።
* ሀገር በቀል እውቀትና ዘመናዊነት፦
የኢትዮጵያን ጥንታዊ የዕርቅና የውይይት እሴቶች ከዘመናዊ ሥርዐተ-ማኅበር ጋር በማቀናጀት የሰላም መሠረት መጣልን ያለመ ነው።
* የባለድርሻ አካላት ሚና፦
ተጽዕኖ ፈጣሪዎች፣ የሃይማኖት አባቶችና የፖለቲካ ፓርቲዎች የምክክሩን አስፈላጊነት ለሕዝብ የማድረስ ታላቅ ኃላፊነት አለባቸው።
* ምርምር ተኮር ውይይት፦
ስሜት ላይ ብቻ ሳይሆን እውቀትና ምርምርን መሠረት ያደረጉ መድረኮችን መፍጠር።
"እውነት ሲገኝ ፍትህ ይነግሳል፤ ፍትህ ሲኖር ደግሞ ሰላም የጸና ይሆናል።" — ዶ/ር ዮናስ
🙏 የእኛ የዜግነት ድርሻ፦
ኢትዮጵያ አሁን ባለችበት ነባራዊ ሁኔታ፣ ካለፈው ቁስል ተፈውሰን ለነገው ትውልድ የምታኮራ ሀገር ለማስተላለፍ የሁላችንም ቅንነትና እውነትን የመቀበል ዝግጁነት ወሳኝ ነው።
ተመካክረን ኢትዮጵያን ለትውልድ እናሻግር
#ሀገራዊምክክር #ኢትዮጵያ #ዘላቂሰላም #እውነት #ፍትህ #nationaldialogue #ethiopia #peacebuilding #dryonasadaye #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን
— ዶ/ር ዮናስ አዳዬ
#ethiopia | በሀገራችን ዘላቂ ሰላም ለመገንባትና ጠንካራ ሀገረ መንግሥት ለመመሥረት ከመመካከር ውጭ አማራጭ እንደሌለ የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ኮሚሽነር ዶ/ር ዮናስ አዳዬ በድጋሚ አስገንዝበዋል።
ዛሬ በአዳማ ከተማ ከሚዲያ ተቋማት ጋር ምክክር እያደረገ ይገኛል።
የምክክሩ ዋና ዓላማዎችና ፋይዳዎች፦
* እውነትን ማፈላለግ፦
ያለፉ ስህተቶችን በቅንነት በመፈተሽ፣ እውነተኛ ታሪክን በመረዳትና መፍትሔዎችን በማመንጨት የጋራ "እውነት" ላይ መድረስ።
* ሀገር በቀል እውቀትና ዘመናዊነት፦
የኢትዮጵያን ጥንታዊ የዕርቅና የውይይት እሴቶች ከዘመናዊ ሥርዐተ-ማኅበር ጋር በማቀናጀት የሰላም መሠረት መጣልን ያለመ ነው።
* የባለድርሻ አካላት ሚና፦
ተጽዕኖ ፈጣሪዎች፣ የሃይማኖት አባቶችና የፖለቲካ ፓርቲዎች የምክክሩን አስፈላጊነት ለሕዝብ የማድረስ ታላቅ ኃላፊነት አለባቸው።
* ምርምር ተኮር ውይይት፦
ስሜት ላይ ብቻ ሳይሆን እውቀትና ምርምርን መሠረት ያደረጉ መድረኮችን መፍጠር።
"እውነት ሲገኝ ፍትህ ይነግሳል፤ ፍትህ ሲኖር ደግሞ ሰላም የጸና ይሆናል።" — ዶ/ር ዮናስ
🙏 የእኛ የዜግነት ድርሻ፦
ኢትዮጵያ አሁን ባለችበት ነባራዊ ሁኔታ፣ ካለፈው ቁስል ተፈውሰን ለነገው ትውልድ የምታኮራ ሀገር ለማስተላለፍ የሁላችንም ቅንነትና እውነትን የመቀበል ዝግጁነት ወሳኝ ነው።
ተመካክረን ኢትዮጵያን ለትውልድ እናሻግር
#ሀገራዊምክክር #ኢትዮጵያ #ዘላቂሰላም #እውነት #ፍትህ #nationaldialogue #ethiopia #peacebuilding #dryonasadaye #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን
6 months ago
የባሕር በር ጥያቄ ምላሽ እንዲያገኝ የክልሉ ሕዝብ የበኩሉን ለመወጣት ዝግጁ ነው - እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህዝብ የባሕር በር ጥያቄ ምላሽ እንዲያገኝ ከመንግሥት ጎን በመቆም የበኩሉን ለመወጣት ዝግጁ ነው አሉ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)።
20ኛው የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን በዓል "ዴሞክራሲያዊ መግባባት ለሕብረ ብሔራዊ አንድነት'' በሚል መሪ ሀሳብ በክልሉ ሆሳዕና ከተማ እየተከበረ ይገኛል።
በበዓሉ ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድን (ዶ/ር) ጨምሮ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች፣ የክልሎች ርዕሳነ መስተዳድሮች፣ የከተማ አስተዳደር ከንቲባዎች፣ የብሔር ብሔረሰቦች ተወካዮች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) በወቅቱ እንዳሉት፤ በዓሉ ብሔራዊ መግባባትን በማጠናከር የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች በአንድ መድረክ ላይ ተገናኝተው እንዲመክሩ እና እንዲደምቁ እድል ፈጥሯል።
እንዲሁም ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ዜጎች መክረው የመፍትሔዎች አካል እንዲሆኑ ለማስቻል፣ የጋራ ትርክትን በጽኑ መሰረት ላይ ለማኖር እና የሀገረ መንግሥትን ቅቡልነት ከፍ ለማድረግ ለተጀመረው ሀገራዊ የምክክር ሂደት የራሱ አስተዋጽዖ ያበረክታል ብለዋል።
ከዚህ በተጨማሪ በዓሉ ባሕላዊ ትውፊቶችን እና ልምዶችን የሚለዋወጡበት ዕድል የፈጠረ መሆኑን ገልጸው፤ ለወንድማማችነት እሴቶች ማበብ እና ለሕብረ ብሔራዊ አንድነት፣ ለፌደራሊዝም ስርዓት መጠናከር እና ለጋራ ትርክት ግንባታ የራሱን አስተዋጽዖ ማበርከቱን ተናግረዋል።
የብሔሮች፣ ብሔረሰቦች እና ህዝቦች በዓል በሀሳብ ልዕልና በመመራት ለብሔራዊ ጥቅም ቅድሚያ በመስጠት የመመካከር እና የመወያየት ባሕልን በማላቅ የዳበረ የዴሞክራሲ እና የአካታችነት እሴቶችን ለማስረጽ እንደ አንድ መልካም አጋጣሚ የሚወሰድ እንደሆነም አመልክተዋል።
የዘንድሮውን በዓል የዘመናት ቁጭት መቋጫ፣ የአዲስ ንጋት ማብሰሪያ እና የማንሰራራት ዘመን ምልክት እና አሻራ የሆነውን የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ምረቃ እና ሌሎች ግዙፍ ሀገራዊ ፕሮጀክቶች በተጀመሩበት ወቅት የሚከበር መሆኑ የተለየ ያደርገዋል ነው ያሉት።
የክልሉ ሕዝብ በጋራ እሴቶች የተሳሰረች፣ በብዝሐነት ያጌጠች፣ በጋራ ትርክት የጸናች፣ በጋራ ሕልም ተስፋዋን ከፍ ለማድረግ የምትተጋ ሕብረ ብሔራዊት ኢትዮጵያን በመገንባቱ ረገድ ከወትሮው በላቀ በታታሪነት እና በትብብር መንፈስ ለመትጋት ዝግጁ መሆኑን አረጋግጠዋል።
በሕብረ ብሔራዊ ፌደራሊዝም ስርዓት የተደነገጉ የራስ አስተዳደር እና የጋራ አስተዳደር ማዕቀፎችን መሰረት አድርጎ በመንቀሳቀስ ማንነት፣ ኢትዮጵያዊነት እና አንድነት ሚዛናቸውን ጠብቀው የሚራመዱበት ጠንካራ ኢትዮጵያን ዕውን በማድረግ ሂደት ላይ ክልሉ የበኩሉን እንደሚወጣ ጠቁመዋል።
ኢትዮጵያ የምግብ ሉዓላዊነትን በጋራ ጥረት ዕውን በማድረግ ሉዓላዊነቷ እና ብሔራዊ ክብሯ የተሟላ ሆኖ የብልጽግና ጉዞዋ እንዲሳካ ክልሉ የጀመረውን ጥረት አጠናክሮ እንደሚያስቀጥል ተናግረዋል።
የሀገራችን ብሔራዊ ጥቅም ለማስጠበቅ እና አዳጊ የሕዝብ ጥቅሞችን ለማስከበር እና አዳጊ የሕዝቦች ፍላጎቶችን ለማሟላት መሰረታዊ የሆነው የባሕር በር ጥያቄ ምላሽ እንዲያገኝ በሚደረገው እንቅስቃሴ የክልሉ ሕዝብ ከመንግሥት ጎን በመቆም የበኩሉን ለመወጣት ዝግጁ ነው ብለዋል።
FBC
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህዝብ የባሕር በር ጥያቄ ምላሽ እንዲያገኝ ከመንግሥት ጎን በመቆም የበኩሉን ለመወጣት ዝግጁ ነው አሉ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)።
20ኛው የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን በዓል "ዴሞክራሲያዊ መግባባት ለሕብረ ብሔራዊ አንድነት'' በሚል መሪ ሀሳብ በክልሉ ሆሳዕና ከተማ እየተከበረ ይገኛል።
በበዓሉ ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድን (ዶ/ር) ጨምሮ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች፣ የክልሎች ርዕሳነ መስተዳድሮች፣ የከተማ አስተዳደር ከንቲባዎች፣ የብሔር ብሔረሰቦች ተወካዮች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) በወቅቱ እንዳሉት፤ በዓሉ ብሔራዊ መግባባትን በማጠናከር የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች በአንድ መድረክ ላይ ተገናኝተው እንዲመክሩ እና እንዲደምቁ እድል ፈጥሯል።
እንዲሁም ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ዜጎች መክረው የመፍትሔዎች አካል እንዲሆኑ ለማስቻል፣ የጋራ ትርክትን በጽኑ መሰረት ላይ ለማኖር እና የሀገረ መንግሥትን ቅቡልነት ከፍ ለማድረግ ለተጀመረው ሀገራዊ የምክክር ሂደት የራሱ አስተዋጽዖ ያበረክታል ብለዋል።
ከዚህ በተጨማሪ በዓሉ ባሕላዊ ትውፊቶችን እና ልምዶችን የሚለዋወጡበት ዕድል የፈጠረ መሆኑን ገልጸው፤ ለወንድማማችነት እሴቶች ማበብ እና ለሕብረ ብሔራዊ አንድነት፣ ለፌደራሊዝም ስርዓት መጠናከር እና ለጋራ ትርክት ግንባታ የራሱን አስተዋጽዖ ማበርከቱን ተናግረዋል።
የብሔሮች፣ ብሔረሰቦች እና ህዝቦች በዓል በሀሳብ ልዕልና በመመራት ለብሔራዊ ጥቅም ቅድሚያ በመስጠት የመመካከር እና የመወያየት ባሕልን በማላቅ የዳበረ የዴሞክራሲ እና የአካታችነት እሴቶችን ለማስረጽ እንደ አንድ መልካም አጋጣሚ የሚወሰድ እንደሆነም አመልክተዋል።
የዘንድሮውን በዓል የዘመናት ቁጭት መቋጫ፣ የአዲስ ንጋት ማብሰሪያ እና የማንሰራራት ዘመን ምልክት እና አሻራ የሆነውን የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ምረቃ እና ሌሎች ግዙፍ ሀገራዊ ፕሮጀክቶች በተጀመሩበት ወቅት የሚከበር መሆኑ የተለየ ያደርገዋል ነው ያሉት።
የክልሉ ሕዝብ በጋራ እሴቶች የተሳሰረች፣ በብዝሐነት ያጌጠች፣ በጋራ ትርክት የጸናች፣ በጋራ ሕልም ተስፋዋን ከፍ ለማድረግ የምትተጋ ሕብረ ብሔራዊት ኢትዮጵያን በመገንባቱ ረገድ ከወትሮው በላቀ በታታሪነት እና በትብብር መንፈስ ለመትጋት ዝግጁ መሆኑን አረጋግጠዋል።
በሕብረ ብሔራዊ ፌደራሊዝም ስርዓት የተደነገጉ የራስ አስተዳደር እና የጋራ አስተዳደር ማዕቀፎችን መሰረት አድርጎ በመንቀሳቀስ ማንነት፣ ኢትዮጵያዊነት እና አንድነት ሚዛናቸውን ጠብቀው የሚራመዱበት ጠንካራ ኢትዮጵያን ዕውን በማድረግ ሂደት ላይ ክልሉ የበኩሉን እንደሚወጣ ጠቁመዋል።
ኢትዮጵያ የምግብ ሉዓላዊነትን በጋራ ጥረት ዕውን በማድረግ ሉዓላዊነቷ እና ብሔራዊ ክብሯ የተሟላ ሆኖ የብልጽግና ጉዞዋ እንዲሳካ ክልሉ የጀመረውን ጥረት አጠናክሮ እንደሚያስቀጥል ተናግረዋል።
የሀገራችን ብሔራዊ ጥቅም ለማስጠበቅ እና አዳጊ የሕዝብ ጥቅሞችን ለማስከበር እና አዳጊ የሕዝቦች ፍላጎቶችን ለማሟላት መሰረታዊ የሆነው የባሕር በር ጥያቄ ምላሽ እንዲያገኝ በሚደረገው እንቅስቃሴ የክልሉ ሕዝብ ከመንግሥት ጎን በመቆም የበኩሉን ለመወጣት ዝግጁ ነው ብለዋል።
FBC
6 months ago
አፍሪካ የሕግ የበላይነትን በማስጠበቅ ዕድገቷን ለማረጋገጥ ወሳኝ ምዕራፍ ላይ ናት - አቶ ቴዎድሮስ ምህረት
#ethiopia | አፍሪካ የሕግ የበላይነትን በማስጠበቅ ልማትና ዕድገቷን ለማረጋገጥ በወሳኝ ምዕራፍ ላይ ትገኛለች አሉ የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት አቶ ቴዎድሮስ ምህረት።
4ኛው የአፍሪካ ህገመንግሥታዊ ፍርድ ቤቶች እና መሰል ተቋማት ዓለም አቀፍ ሲምፖዝየም ‘ህገ መንግሥታዊነት እና ሀገረ መንግሥት ግንባታ’ በሚል መሪ ሀሳብ በአዲስ አበባ መካሄድ ጀምሯል።
አቶ ቴዎድሮስ ምህረት በዚሁ ወቅት፤ አፍሪካ ለሕገ-መንግሥታዊነት እና ለሀገረ መንግሥት ግንባታ የጀመረችውን ጥረት አጠናክራ ማስቀጠል ይኖርባታል ብለዋል፡፡
አፍሪካ ቁልፍ የሕዝብ አገልግሎቶችን መስጠት የሚችሉ የተረጋጋ ተቋማትን በመገንባት እና ተቋማዊ በማድረግ ረገድ በስፋት መስራት እንደሚጠበቅባት ገልጸዋል፡፡
የሕግ የበላይነትን ማረጋገጥና የሰብአዊ መብቶችን ለማጠናከር የአስተዳደር ሁኔታን ከማሻሻል ባሻገር የአህጉሪቱን ልማት ማፋጠን መሠረታዊ ጉዳዮች መሆናቸውን አብራርተዋል።
የዚምባብዌ ጠቅላይ ዳኛ እና የአፍሪካ የሕገ መንግሥት የዳኝነት አካላት ጉባኤ ፕሬዚዳንት ሉክ ማላባ በበኩላቸው÷ አፍሪካውያን በራሳቸው መተማመንና የለውጥ አጀንዳቸውን መምራት እንደሚገባቸው አጽንኦት ሰጥተዋል።
የአፍሪካ ህብረትን መሠረታዊ መርሆች ማስጠበቅ እና አፍሪካውያን የራሳቸውን የለውጥ አጀንዳዎች መምራት እንዲችሉ ማድረግ እንደሚገባም ማስገንዘባቸውን #ኢዜአ ዘግቧል፡፡
#ethiopia | አፍሪካ የሕግ የበላይነትን በማስጠበቅ ልማትና ዕድገቷን ለማረጋገጥ በወሳኝ ምዕራፍ ላይ ትገኛለች አሉ የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት አቶ ቴዎድሮስ ምህረት።
4ኛው የአፍሪካ ህገመንግሥታዊ ፍርድ ቤቶች እና መሰል ተቋማት ዓለም አቀፍ ሲምፖዝየም ‘ህገ መንግሥታዊነት እና ሀገረ መንግሥት ግንባታ’ በሚል መሪ ሀሳብ በአዲስ አበባ መካሄድ ጀምሯል።
አቶ ቴዎድሮስ ምህረት በዚሁ ወቅት፤ አፍሪካ ለሕገ-መንግሥታዊነት እና ለሀገረ መንግሥት ግንባታ የጀመረችውን ጥረት አጠናክራ ማስቀጠል ይኖርባታል ብለዋል፡፡
አፍሪካ ቁልፍ የሕዝብ አገልግሎቶችን መስጠት የሚችሉ የተረጋጋ ተቋማትን በመገንባት እና ተቋማዊ በማድረግ ረገድ በስፋት መስራት እንደሚጠበቅባት ገልጸዋል፡፡
የሕግ የበላይነትን ማረጋገጥና የሰብአዊ መብቶችን ለማጠናከር የአስተዳደር ሁኔታን ከማሻሻል ባሻገር የአህጉሪቱን ልማት ማፋጠን መሠረታዊ ጉዳዮች መሆናቸውን አብራርተዋል።
የዚምባብዌ ጠቅላይ ዳኛ እና የአፍሪካ የሕገ መንግሥት የዳኝነት አካላት ጉባኤ ፕሬዚዳንት ሉክ ማላባ በበኩላቸው÷ አፍሪካውያን በራሳቸው መተማመንና የለውጥ አጀንዳቸውን መምራት እንደሚገባቸው አጽንኦት ሰጥተዋል።
የአፍሪካ ህብረትን መሠረታዊ መርሆች ማስጠበቅ እና አፍሪካውያን የራሳቸውን የለውጥ አጀንዳዎች መምራት እንዲችሉ ማድረግ እንደሚገባም ማስገንዘባቸውን #ኢዜአ ዘግቧል፡፡
11 months ago
“ሥልጣኔዎቿ ከባሕር ጋር ይያያዛሉ፣ ታሪኮቿ ከባሕር ጋር ይተሳሠራሉ”
#ethiopia | እርሷ ባሕሩን ከየብሱ ጋር አስማምታ ገዝታለች፤ ሀገረ መንግሥትን ከዘመናት በፊት አጽንታለች፤ ሕግና ሥርዓትን አስተምራለች፡፡
ለዘመናት በረቀቀ እና በጸና ሥርዓት ኖራለች፡፡ ጥላ ላጡት ጥላና ከለላ ኾናለች፡፡ አርዓያና ምሳሌ ተደርጋ በዓለሙ ሁሉ ተጠርታለች፡፡ መንገድ ለጠፋባቸው መንገድ አሳይታለች፤ ሥልጣኔ ለራቃቸው የሥልጣኔን መስመር አስተምራለች፡፡
በጥበብ እና በሥልጣኔ ጎዳናዎች ተረማምዳለች፤ የድል አድራጊነት ሐውልቶችን አቁማለች። ከዓለሙ በተለየ ኪነ ሕንጻን አንጻለች። ነጻነትን ከዓለት አጠንክራ አጽንታለች፤ በነጻነት ላይ የመጡባትን ሁሉ ድል መትታለች፤ እርሷ በባሕር ንግድ የዓለም ዳርቻዎችን አካልላለች፡፡
በእርሷ ምድር ብቻ የሚገኙትን ዕንቁ ሀብቶች በባሕር እና በየብስ ለዓለሙ ገበያ አቅርባለች፡፡ ከዓለም ዳርቻዎች የሚመጡትን ነጋዴዎችም በወደቦቿ ተቀብላለች፡፡ በጎዳናዎቿም በሰላም እንዲመላለሱ ፈቅዳለች፡፡
በበዙት ወደቦቿ የሚወጣውን ሸኝታለች፤ የሚገባውን ተቀብላለች፡፡ በየብሱ እና በባሕሩ በገነባችው ሠራዊት ሉዓላዊነቷን አስጠብቃ ዘመናትን ተሻግራለች፡፡ አይነኬ ሀገርነቷን በዓለሙ ሁሉ አስመስክራለች። ሥልጣኔዎቿ ከባሕር ጋር ይያያዛሉ፡፡ ታሪኮቿ ከባሕር ጋር ይተሳሰራሉ፡፡ እርሷን ያለ ባሕር ማሰብ አይቻልም፡፡
ቀይ ባሕር ቀለሟ ነው ታሪኳን የጻፈችበት፣ ቀይ ባሕር ብራናዋ ነው ታሪኳን ያሰፈረችበት፣ ቀይ ባሕር ማንነቷ ነው ሥልጣኔዎቿን ያሳያችበት፤ ቀይ ባሕር መንገዷ ነው ወደ ከፍታ የተጓዘችበት፤ ቀይ ባሕር ድልድዩዋ ነው ከዓለማት ጋር የተገናኘችበት፣ ቀይ ባሕር ማሕተሟ ነው የታሪክ እውነታዎቿን ያተመችበት፣ ቀይ ባሕር አዋጅ ነጋሪዋ ነው ታላቅነቷን ለዓለም ሁሉ የነገረችበት፣ ቀይ ባሕር እልፍኟ ነው የውጩ እና የውስጡን ያሰባሰበችበት።
ኢትዮጵያ በቀይ ባሕር እና አካባቢው ያለውን ግዛቷን ባሕረ ነጋሽ እያለች ስታስተዳድር ኖራለች። ይህም እስከ ደርግ ዘመነ መንግሥት ፍጻሜ ድረስ ቀጥሏል። ኢትዮጵያ እና ቀይ ባሕር በታሪክ እና በማንነት ባይለያዩም፣ ቀይ ባሕር ያለ ኢትዮጵያ ባይታሰብም፣ ኢትዮጵያም ያለ ቀይ ባሕር ታሪኳ ባይነገርም ለዓመታት ሃብቷን አጥታ ኖራለች። ይህም ብዙ አጉድሎባታል።
የቀድሞ የኢትዮጵያ ክፍለ ሀገር ባሕረ ነጋሽ የአሁኗ ኤርትራ ሀገር ከኾነች ጀምሮ ኢትዮጵያ ታሪክ የቀመረችባቸውን፣ ሥልጣኔዋን ከፍ ከፍ ያደረገችባቸውን፣ ጥበብ እና ሃይማኖት የነገረችባቸውን፣ ወዳጆቿን የተቀበለችባቸውን ወደቦቿን አጥታ ኖራለች። ይህም ብዙ አጉድሎባታል።
የአፍሪካ አብነት፣ የጥቁሮች እመቤት የኾነችው ኢትዮጵያ ታላላቆች ልጆቿ አስከብረውት የኖሩት የታሪኳ እና የማንነቷ ውብ ቀለም ቀይ ባሕር ያስፈልጋታል። የእርሷ ነበርና ለእርሷ ይገባታል።
ቀኝ አዝማች ታደሰ ዘወልዴ የእቴጌ ጣይቱ ብጡል አጭር የሕይወት ታሪክ በተሰኘው መጽሐፋቸው ሰው ሁሉ በተፈጥሮው እኩልነት ያለው ነው፡፡ በታሪኩ ግን ይለያያል፡፡ አንዱ ከአንዱ በልጦ ይገኛል፡፡ አንዱ ለቆመለት ከፍተኛ ዓላማ የግል ጥቅሙን መስዋዕት ለማድረግ የሚያበቃው ጀግንነት ሲኖረው ሌላው ተቃራኒው ፈለግ በመከተል ኑሮውን ይመራል፡፡
የጀግና ልቦና ለሀገሬ እንጂ ለራሴ ከሚል ግላዊ ሀሳብ የራቀ ነው ይላሉ፡፡ ኢትዮጵያውያን ጀግኖችም ለሀገሬ እንጂ ለራሴ ከሚል ግላዊ እሳቤ ወጥተው ለኢትዮጵያ ኖረዋል፤ ስለ ኢትዮጵያ አልፈዋል፡፡ ኢትዮጵያ የምትከበርበትን እና ከፍ ከፍ የምትልበትን አድርገዋል። ሁሉንም ለሀገራቸው ሰጥተዋል፡፡ ነፍሳቸውን ሳይቀር ለኢትዮጵያ ከፍታና ልዕልና አድርገዋል፡፡
በተቃራኒው ደግሞ ለራሴ በሚል ግላዊ እሳቤ የነበሩ ጥቂቶች ደግሞ ኢትዮጵያን ብዙ ነገር አሳጥተዋል። ለዚህ ማሳያው ደግሞ ቀይ ባሕርን ያጣችበት መንገድ ነው። በዚህ ዘመን ደግሞ ቀይ ባሕር ለኢትዮጵያ እንደሚያስፈልጋት እና እንደሚገባት በግልጽ የጠየቁ መሪዎች መጥተዋል። ይህም ከራስ አልፎ ለሀገር እና ለወገን ማሳብ ነው።
ሐሪ አትክንስ የኢትዮጵያ ታሪክ በተሰኘው መጽሐፋቸው ኢትዮጵያን የባሕር በር ያላት፣ ጥንታዊት ሀገር መኾኗን ጽፈዋል፡፡ እርሷ ከቀደሙ ጥንታውያን ሥልጣኔ ከነበራቸው ሀገራት በአዶሊስ እና በሌሎች ወደቦቿ አማካኝነት በመርከብ ንግድ ታሳልጥ እንደነበር እና ከሀገራት ጋር ጥብቅ ግንኙነት ታደርግ እንደነበር መዝግበዋል፡፡
የኢትዮጵያ ታሪክ ከተመዘገበበት ዘመን ጀምሮ ቀይ ባሕር ብቻ ሳይኾን ከቀይ ባሕር ባሻገር የነበሩ ሀገራትም የኢትዮጵያ እና የኢትዮጵያውያን እንደነበሩ ሲነገር ኖሯል። ለዚህም ደግሞ በዓላት ላይ የተቀረጹ፣ በብራና የሰፈሩ፣ በወረቀት የተከተቡ አያሌ ማስረጃዎች ሞልተዋል። ይህ ብቻ አይደለም በሕይወት ያሉ አያሌ ሰዎችም ኢትዮጵያ እና ቀይ ባሕር እንደማይነጣጠሉ ዛሬም በሕይወት ይመሰክራሉ።
የፖለቲካ ሳይንስ ምሁሩ ፕሮፌሰር ቡሩክ ኃይሉ ኢትዮጵያ የኋላ ታሪኳ ሲነገር፣ ሥልጣኔዋ ሲመዘዝ የዳህላክ፣ የአዶሊስ እና የሌሎች ወደቦች ባለቤት እንደነበረች፣ በባሕሯ በቀይ ባሕር አማካኝነት ከግሪክ እና ከሮማውያን ጋር ትገናኝ ነበር ነው የሚሉት፡፡
የሺህ ዘመናት ታሪኳ ሲነገር ኢትዮጵያ እና ባሕር በር አይነጣጠሉም፡፡ እርሷ አንድ ብቻ ሳይኾን በርከት ያሉ ወደቦች የነበሯት ሀገር ናት ይላሉ፡፡
ኢትዮጵያ በባሕር ላይ ሥልጣኔዋ በታሪክ አንቱ የተባለች ናት፡፡ የቀይ ባሕር ባለቤት ብቻ ሳትኾን ከዚያም ተሻግራ ሀገራትን ታስተዳድር እንደነበር ታሪክ ይመዝዛሉ፡፡ ቀይ ባሕር ቤቷ፣ መግቢያ እና መውጫዋ ነው ይላሉ፡፡ የቀይ ባሕር ለኢትዮጵያ እንደ አዲስ የሚተረክ አይደለም የእርሷ ነውና፡፡
ኢትዮጵያ ከጥቂት ዓመታት ወዲህ ነው የባሕር በር ያጣችው የሚሉት ምሁሩ አሁን ላይ የራሷ የነበረውን የባሕር በር እንደሚገባት በግልጽ ጠይቃለች፤ ጥያቄዋም ታሪካዊ፣ ሕጋዊ እና እውነትን መሠረት ያደረገ ነው ይላሉ፡፡ የኢትዮጵያን የባሕር በር ጥያቄ ዓለም አቀፍ ሕግም እንደሚደግፋት ተናግረዋል፡፡
ኢትዮጵያ እንደማንኛውም ሀገር የባሕር በር ያስፈልጋታል፡፡ ይገባታልም ይላሉ፡፡ ኢትዮጵያ እስካኹን ድረስ መጠቀም የሚገባትን ሳትጠቀም ቆይታለች፤ በሚያሳዝን ኹኔታ የባሕር በሯን ተነጥቃ ቆይታለች ነው የሚሉት፡፡
የኢትዮጵያ አኹናዊ ቁልፍ የዲፕሎማሲ ሥራ ታላቋ፣ ታሪካዊቷ እና ጥንታዊቷ ሀገር የባሕር በር እንዲኖራት ማድረግ ነው ይላሉ፡፡ ኢትዮጵያ የባሕር በር ማግኘት እንዳለባት፣ በዚህ መንገድ ታፍና መኖር እንደሌለባት እየተሠራ ነው፤ ኢትዮጵያ በሰላማዊ መንገድ የባሕር በር ለማግኘት ጥረት ታደርጋለች፤ ጥረቷን ከጎረቤቶቿ ሀገራት ጋር አጠናክራ ትቀጥላለች ይላሉ፡፡
ኢትዮጵያ ለባሕር በር የቀረበች መኾኗን ነው የተናገሩት፡፡ በርካታ ሀገራትም የኢትዮጵያ የባሕር በር ጥያቄ ፍትሐዊ እንደኾነ፣ የኢትዮጵያ የባሕር በር ጥያቄ ማግኘት ለቀጣናው ሰላምና መረጋጋት ትልቅ አስተዋጽኦ እንደሚያደርግ እየገለጹ ነው ይላሉ፡፡
ሕዝብ እና መንግሥት ሲናበቡ ታላላቅ ሥራዎችን ይሠራሉ የሚሉት ምሁሩ የፖለቲካዊ ልዩነቶች ሊኖሩ ይችላሉ፤ ነገር ግን በሀገራዊ ጉዳይ ልዩነት ሊኖር አይገባም፣ ኢትዮጵያውያን አንድ ሲኾኑ የማይሠሩት ታላቅ ሥራ የለም ነው የሚሉት፡፡ ሀገርን በማስቀደም፣ ሀገር የምትጠይቀውን በመስጠት የታሰበውን ማስፈጸም የዚህ ዘመን ትውልድ አደራ ነው ብለዋል።
የኢትዮጵያ የባሕር በር ጥያቄ የዚህ ዘመን መንግሥት ጥያቄ ብቻ አይደለም፣ የኢትዮጵያ እና የኢትዮጵያውያን ጥያቄ ነው፤ መንግሥት በሕዝብ ተደግፎ ሲሠራ የባሕር በር ጥያቄው ይሳካል ነው የሚሉት፡፡
ወጥ እና የተባባረ ኀይል ይዘን ከቀጥልን የትኛውም ችግር ሊበግረን አይችልም ይላሉ፡፡ የባሕር በር ጥያቄ የሀገር እና የሕዝብ ጥያቄ ነው። ጥቅሙም ለሕዝብ እና ለሀገር ነው። የቀደመውን ታሪክ እና ታላቅነት ለመመለስ በአንድነት እና በፍቅር ሰላማዊ በኾነ መንገድ መሥራት የዚህ ዘመን ትውልድ አደራ ነው።
በታርቆ ክንዴ #amico
#ethiopia | እርሷ ባሕሩን ከየብሱ ጋር አስማምታ ገዝታለች፤ ሀገረ መንግሥትን ከዘመናት በፊት አጽንታለች፤ ሕግና ሥርዓትን አስተምራለች፡፡
ለዘመናት በረቀቀ እና በጸና ሥርዓት ኖራለች፡፡ ጥላ ላጡት ጥላና ከለላ ኾናለች፡፡ አርዓያና ምሳሌ ተደርጋ በዓለሙ ሁሉ ተጠርታለች፡፡ መንገድ ለጠፋባቸው መንገድ አሳይታለች፤ ሥልጣኔ ለራቃቸው የሥልጣኔን መስመር አስተምራለች፡፡
በጥበብ እና በሥልጣኔ ጎዳናዎች ተረማምዳለች፤ የድል አድራጊነት ሐውልቶችን አቁማለች። ከዓለሙ በተለየ ኪነ ሕንጻን አንጻለች። ነጻነትን ከዓለት አጠንክራ አጽንታለች፤ በነጻነት ላይ የመጡባትን ሁሉ ድል መትታለች፤ እርሷ በባሕር ንግድ የዓለም ዳርቻዎችን አካልላለች፡፡
በእርሷ ምድር ብቻ የሚገኙትን ዕንቁ ሀብቶች በባሕር እና በየብስ ለዓለሙ ገበያ አቅርባለች፡፡ ከዓለም ዳርቻዎች የሚመጡትን ነጋዴዎችም በወደቦቿ ተቀብላለች፡፡ በጎዳናዎቿም በሰላም እንዲመላለሱ ፈቅዳለች፡፡
በበዙት ወደቦቿ የሚወጣውን ሸኝታለች፤ የሚገባውን ተቀብላለች፡፡ በየብሱ እና በባሕሩ በገነባችው ሠራዊት ሉዓላዊነቷን አስጠብቃ ዘመናትን ተሻግራለች፡፡ አይነኬ ሀገርነቷን በዓለሙ ሁሉ አስመስክራለች። ሥልጣኔዎቿ ከባሕር ጋር ይያያዛሉ፡፡ ታሪኮቿ ከባሕር ጋር ይተሳሰራሉ፡፡ እርሷን ያለ ባሕር ማሰብ አይቻልም፡፡
ቀይ ባሕር ቀለሟ ነው ታሪኳን የጻፈችበት፣ ቀይ ባሕር ብራናዋ ነው ታሪኳን ያሰፈረችበት፣ ቀይ ባሕር ማንነቷ ነው ሥልጣኔዎቿን ያሳያችበት፤ ቀይ ባሕር መንገዷ ነው ወደ ከፍታ የተጓዘችበት፤ ቀይ ባሕር ድልድዩዋ ነው ከዓለማት ጋር የተገናኘችበት፣ ቀይ ባሕር ማሕተሟ ነው የታሪክ እውነታዎቿን ያተመችበት፣ ቀይ ባሕር አዋጅ ነጋሪዋ ነው ታላቅነቷን ለዓለም ሁሉ የነገረችበት፣ ቀይ ባሕር እልፍኟ ነው የውጩ እና የውስጡን ያሰባሰበችበት።
ኢትዮጵያ በቀይ ባሕር እና አካባቢው ያለውን ግዛቷን ባሕረ ነጋሽ እያለች ስታስተዳድር ኖራለች። ይህም እስከ ደርግ ዘመነ መንግሥት ፍጻሜ ድረስ ቀጥሏል። ኢትዮጵያ እና ቀይ ባሕር በታሪክ እና በማንነት ባይለያዩም፣ ቀይ ባሕር ያለ ኢትዮጵያ ባይታሰብም፣ ኢትዮጵያም ያለ ቀይ ባሕር ታሪኳ ባይነገርም ለዓመታት ሃብቷን አጥታ ኖራለች። ይህም ብዙ አጉድሎባታል።
የቀድሞ የኢትዮጵያ ክፍለ ሀገር ባሕረ ነጋሽ የአሁኗ ኤርትራ ሀገር ከኾነች ጀምሮ ኢትዮጵያ ታሪክ የቀመረችባቸውን፣ ሥልጣኔዋን ከፍ ከፍ ያደረገችባቸውን፣ ጥበብ እና ሃይማኖት የነገረችባቸውን፣ ወዳጆቿን የተቀበለችባቸውን ወደቦቿን አጥታ ኖራለች። ይህም ብዙ አጉድሎባታል።
የአፍሪካ አብነት፣ የጥቁሮች እመቤት የኾነችው ኢትዮጵያ ታላላቆች ልጆቿ አስከብረውት የኖሩት የታሪኳ እና የማንነቷ ውብ ቀለም ቀይ ባሕር ያስፈልጋታል። የእርሷ ነበርና ለእርሷ ይገባታል።
ቀኝ አዝማች ታደሰ ዘወልዴ የእቴጌ ጣይቱ ብጡል አጭር የሕይወት ታሪክ በተሰኘው መጽሐፋቸው ሰው ሁሉ በተፈጥሮው እኩልነት ያለው ነው፡፡ በታሪኩ ግን ይለያያል፡፡ አንዱ ከአንዱ በልጦ ይገኛል፡፡ አንዱ ለቆመለት ከፍተኛ ዓላማ የግል ጥቅሙን መስዋዕት ለማድረግ የሚያበቃው ጀግንነት ሲኖረው ሌላው ተቃራኒው ፈለግ በመከተል ኑሮውን ይመራል፡፡
የጀግና ልቦና ለሀገሬ እንጂ ለራሴ ከሚል ግላዊ ሀሳብ የራቀ ነው ይላሉ፡፡ ኢትዮጵያውያን ጀግኖችም ለሀገሬ እንጂ ለራሴ ከሚል ግላዊ እሳቤ ወጥተው ለኢትዮጵያ ኖረዋል፤ ስለ ኢትዮጵያ አልፈዋል፡፡ ኢትዮጵያ የምትከበርበትን እና ከፍ ከፍ የምትልበትን አድርገዋል። ሁሉንም ለሀገራቸው ሰጥተዋል፡፡ ነፍሳቸውን ሳይቀር ለኢትዮጵያ ከፍታና ልዕልና አድርገዋል፡፡
በተቃራኒው ደግሞ ለራሴ በሚል ግላዊ እሳቤ የነበሩ ጥቂቶች ደግሞ ኢትዮጵያን ብዙ ነገር አሳጥተዋል። ለዚህ ማሳያው ደግሞ ቀይ ባሕርን ያጣችበት መንገድ ነው። በዚህ ዘመን ደግሞ ቀይ ባሕር ለኢትዮጵያ እንደሚያስፈልጋት እና እንደሚገባት በግልጽ የጠየቁ መሪዎች መጥተዋል። ይህም ከራስ አልፎ ለሀገር እና ለወገን ማሳብ ነው።
ሐሪ አትክንስ የኢትዮጵያ ታሪክ በተሰኘው መጽሐፋቸው ኢትዮጵያን የባሕር በር ያላት፣ ጥንታዊት ሀገር መኾኗን ጽፈዋል፡፡ እርሷ ከቀደሙ ጥንታውያን ሥልጣኔ ከነበራቸው ሀገራት በአዶሊስ እና በሌሎች ወደቦቿ አማካኝነት በመርከብ ንግድ ታሳልጥ እንደነበር እና ከሀገራት ጋር ጥብቅ ግንኙነት ታደርግ እንደነበር መዝግበዋል፡፡
የኢትዮጵያ ታሪክ ከተመዘገበበት ዘመን ጀምሮ ቀይ ባሕር ብቻ ሳይኾን ከቀይ ባሕር ባሻገር የነበሩ ሀገራትም የኢትዮጵያ እና የኢትዮጵያውያን እንደነበሩ ሲነገር ኖሯል። ለዚህም ደግሞ በዓላት ላይ የተቀረጹ፣ በብራና የሰፈሩ፣ በወረቀት የተከተቡ አያሌ ማስረጃዎች ሞልተዋል። ይህ ብቻ አይደለም በሕይወት ያሉ አያሌ ሰዎችም ኢትዮጵያ እና ቀይ ባሕር እንደማይነጣጠሉ ዛሬም በሕይወት ይመሰክራሉ።
የፖለቲካ ሳይንስ ምሁሩ ፕሮፌሰር ቡሩክ ኃይሉ ኢትዮጵያ የኋላ ታሪኳ ሲነገር፣ ሥልጣኔዋ ሲመዘዝ የዳህላክ፣ የአዶሊስ እና የሌሎች ወደቦች ባለቤት እንደነበረች፣ በባሕሯ በቀይ ባሕር አማካኝነት ከግሪክ እና ከሮማውያን ጋር ትገናኝ ነበር ነው የሚሉት፡፡
የሺህ ዘመናት ታሪኳ ሲነገር ኢትዮጵያ እና ባሕር በር አይነጣጠሉም፡፡ እርሷ አንድ ብቻ ሳይኾን በርከት ያሉ ወደቦች የነበሯት ሀገር ናት ይላሉ፡፡
ኢትዮጵያ በባሕር ላይ ሥልጣኔዋ በታሪክ አንቱ የተባለች ናት፡፡ የቀይ ባሕር ባለቤት ብቻ ሳትኾን ከዚያም ተሻግራ ሀገራትን ታስተዳድር እንደነበር ታሪክ ይመዝዛሉ፡፡ ቀይ ባሕር ቤቷ፣ መግቢያ እና መውጫዋ ነው ይላሉ፡፡ የቀይ ባሕር ለኢትዮጵያ እንደ አዲስ የሚተረክ አይደለም የእርሷ ነውና፡፡
ኢትዮጵያ ከጥቂት ዓመታት ወዲህ ነው የባሕር በር ያጣችው የሚሉት ምሁሩ አሁን ላይ የራሷ የነበረውን የባሕር በር እንደሚገባት በግልጽ ጠይቃለች፤ ጥያቄዋም ታሪካዊ፣ ሕጋዊ እና እውነትን መሠረት ያደረገ ነው ይላሉ፡፡ የኢትዮጵያን የባሕር በር ጥያቄ ዓለም አቀፍ ሕግም እንደሚደግፋት ተናግረዋል፡፡
ኢትዮጵያ እንደማንኛውም ሀገር የባሕር በር ያስፈልጋታል፡፡ ይገባታልም ይላሉ፡፡ ኢትዮጵያ እስካኹን ድረስ መጠቀም የሚገባትን ሳትጠቀም ቆይታለች፤ በሚያሳዝን ኹኔታ የባሕር በሯን ተነጥቃ ቆይታለች ነው የሚሉት፡፡
የኢትዮጵያ አኹናዊ ቁልፍ የዲፕሎማሲ ሥራ ታላቋ፣ ታሪካዊቷ እና ጥንታዊቷ ሀገር የባሕር በር እንዲኖራት ማድረግ ነው ይላሉ፡፡ ኢትዮጵያ የባሕር በር ማግኘት እንዳለባት፣ በዚህ መንገድ ታፍና መኖር እንደሌለባት እየተሠራ ነው፤ ኢትዮጵያ በሰላማዊ መንገድ የባሕር በር ለማግኘት ጥረት ታደርጋለች፤ ጥረቷን ከጎረቤቶቿ ሀገራት ጋር አጠናክራ ትቀጥላለች ይላሉ፡፡
ኢትዮጵያ ለባሕር በር የቀረበች መኾኗን ነው የተናገሩት፡፡ በርካታ ሀገራትም የኢትዮጵያ የባሕር በር ጥያቄ ፍትሐዊ እንደኾነ፣ የኢትዮጵያ የባሕር በር ጥያቄ ማግኘት ለቀጣናው ሰላምና መረጋጋት ትልቅ አስተዋጽኦ እንደሚያደርግ እየገለጹ ነው ይላሉ፡፡
ሕዝብ እና መንግሥት ሲናበቡ ታላላቅ ሥራዎችን ይሠራሉ የሚሉት ምሁሩ የፖለቲካዊ ልዩነቶች ሊኖሩ ይችላሉ፤ ነገር ግን በሀገራዊ ጉዳይ ልዩነት ሊኖር አይገባም፣ ኢትዮጵያውያን አንድ ሲኾኑ የማይሠሩት ታላቅ ሥራ የለም ነው የሚሉት፡፡ ሀገርን በማስቀደም፣ ሀገር የምትጠይቀውን በመስጠት የታሰበውን ማስፈጸም የዚህ ዘመን ትውልድ አደራ ነው ብለዋል።
የኢትዮጵያ የባሕር በር ጥያቄ የዚህ ዘመን መንግሥት ጥያቄ ብቻ አይደለም፣ የኢትዮጵያ እና የኢትዮጵያውያን ጥያቄ ነው፤ መንግሥት በሕዝብ ተደግፎ ሲሠራ የባሕር በር ጥያቄው ይሳካል ነው የሚሉት፡፡
ወጥ እና የተባባረ ኀይል ይዘን ከቀጥልን የትኛውም ችግር ሊበግረን አይችልም ይላሉ፡፡ የባሕር በር ጥያቄ የሀገር እና የሕዝብ ጥያቄ ነው። ጥቅሙም ለሕዝብ እና ለሀገር ነው። የቀደመውን ታሪክ እና ታላቅነት ለመመለስ በአንድነት እና በፍቅር ሰላማዊ በኾነ መንገድ መሥራት የዚህ ዘመን ትውልድ አደራ ነው።
በታርቆ ክንዴ #amico
Sponsored by
Surafel
Comments