7 days ago
በአሰቃቂ የትራፊክ አደጋ የ11 ሰዎች ሕይወት አለፈ
#ethiopia | ከአልቾ ውሪሮ ወረዳ 18 ተጓዦችን አሳፍሮ በጠረጋ ከተማ በኩል ወደ ዋና ከተማዋ አዲስ አበባ በመጓዝ ላይ የነበረ አንድ አነስተኛ የህዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪ ከሰዓታት በፊት ከመስመር ውጭ በመውጣት ወደ ገደል ወድቋል።
በዚህ አሰቃቂ አደጋም በሰው ህይወትና በንብረት ላይ ከፍተኛ ውድመት ደርሷል።
በደረሰው አደጋ ምክንያት እናቶች፣ ህጻናት፣ ወጣቶችና አባቶችን ያካተቱ 11 ተጓዦች ህይወታቸውን ያጡ ሲሆን፣ ከአሽከርካሪ ጋር ሌላ ሁለት ሰዎች በድምሩ ሦስት ግለሰቦች ላይ ከባድ የአካል ጉዳት ደርሶ የህክምና እርዳታ እየተደረገላቸው ይገኛል።
በአንጻሩ ሁለት ህጻናትን ጨምሮ አራት ተጓዦች ከአደጋው ምንም አይነት ጉዳት ሳይደርስባቸው በሰላም ለመትረፍ ችለዋል።
የአልቾ ውሪሮ ወረዳ አስተዳደር በአደጋው ህይወታቸውን ያጡትን ወገኖች አስክሬን ከቡታጀራ ሆስፒታል ወደ ወራቤ ኮምፕሬሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል በማጓጓዝ ለቤተሰቦቻቸው የማስረከብ ስራ እየሰራ መሆኑን አስታውቋል።
በተመሳሳይ ሁኔታ ከባድ ጉዳት የደረሰባቸው ወገኖች በቡታጀራ እና በወራቤ ሆስፒታሎች ተገቢውን የህክምና ክትትል እንዲያገኙ በማድረግ ላይ ይገኛል።
#trafficaccident #roadsafe #ethiopianews #wolaita #butajira #worabe #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | ከአልቾ ውሪሮ ወረዳ 18 ተጓዦችን አሳፍሮ በጠረጋ ከተማ በኩል ወደ ዋና ከተማዋ አዲስ አበባ በመጓዝ ላይ የነበረ አንድ አነስተኛ የህዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪ ከሰዓታት በፊት ከመስመር ውጭ በመውጣት ወደ ገደል ወድቋል።
በዚህ አሰቃቂ አደጋም በሰው ህይወትና በንብረት ላይ ከፍተኛ ውድመት ደርሷል።
በደረሰው አደጋ ምክንያት እናቶች፣ ህጻናት፣ ወጣቶችና አባቶችን ያካተቱ 11 ተጓዦች ህይወታቸውን ያጡ ሲሆን፣ ከአሽከርካሪ ጋር ሌላ ሁለት ሰዎች በድምሩ ሦስት ግለሰቦች ላይ ከባድ የአካል ጉዳት ደርሶ የህክምና እርዳታ እየተደረገላቸው ይገኛል።
በአንጻሩ ሁለት ህጻናትን ጨምሮ አራት ተጓዦች ከአደጋው ምንም አይነት ጉዳት ሳይደርስባቸው በሰላም ለመትረፍ ችለዋል።
የአልቾ ውሪሮ ወረዳ አስተዳደር በአደጋው ህይወታቸውን ያጡትን ወገኖች አስክሬን ከቡታጀራ ሆስፒታል ወደ ወራቤ ኮምፕሬሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል በማጓጓዝ ለቤተሰቦቻቸው የማስረከብ ስራ እየሰራ መሆኑን አስታውቋል።
በተመሳሳይ ሁኔታ ከባድ ጉዳት የደረሰባቸው ወገኖች በቡታጀራ እና በወራቤ ሆስፒታሎች ተገቢውን የህክምና ክትትል እንዲያገኙ በማድረግ ላይ ይገኛል።
#trafficaccident #roadsafe #ethiopianews #wolaita #butajira #worabe #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
5 months ago
የወላይታ ሶዶ ዓለም አቀፍ ስታዲየም ግንባታ በይፋ ተጀመረ!
#ethiopia | "የወላይታን ባህልና ታሪክ የያዘ፣ ከ40 እስከ 45 ሺህ ተመልካች የሚይዝ ግዙፍ ስታዲየም" በጉጉት ሲጠበቅ የነበረው የወላይታ ሶዶ ዓለም አቀፍ ስታዲየም ግንባታ ዛሬ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ክቡር አቶ ጥላሁን ከበደ፣ በባህልና ስፖርት ሚኒስትር ወ/ሮ ሸዊት ሻንካ እና በወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ረዳት ፕሮፌሰር ሳሙኤል ተሰማ አማካኝነት የመሰረት ድንጋይ ተቀምጦለታል።
የስታዲየሙ ገፅታዎች:
✅ ደረጃ: የፊፋ (FIFA) እና የካፍ (CAF) ስታንዳርድን ያሟላ።
✅ አቅም: ከ40,000 እስከ 45,000 በላይ ተመልካቾችን የመያዝ አቅም አለው።
✅ ዲዛይን: የወላይታን ህዝብ ታሪክ፣ ባህላዊ እሴቶች እና የአካባቢውን ገፅታ ያካተተ ነው።
✅ ይዞታ: በ51 ሄክታር መሬት ላይ የሚያርፍ ይሆናል።
ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ፤ "ይህ ፕሮጀክት የህዝብ ነው፤ ከተባበርንና ካስተባበርን እውን ማድረግ ይቻላል" በማለት፤ የክልሉ መንግስት ለፕሮጀክቱ የሚሆን ልዩ የገቢ ማሰባሰቢያ መርሃ ግብር እንደሚያዘጋጅ ገልጸዋል።
የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ ረዳት ፕሮፌሰር ሳሙኤል ተሰማ በበኩላቸው፤ "እንደጀመርነው እንጨርሰዋለን!" በማለት መላው ህዝብ አሻራውን እንዲያሳርፍ ጥሪ አቅርበዋል።
ዎጌታ ኤፍ ኤም 96.6
#wolaita #stadium #construction #ethiopia
#wolaitasodo #internationalstadium #ethiopia #development #sports #southethiopia
#ethiopia | "የወላይታን ባህልና ታሪክ የያዘ፣ ከ40 እስከ 45 ሺህ ተመልካች የሚይዝ ግዙፍ ስታዲየም" በጉጉት ሲጠበቅ የነበረው የወላይታ ሶዶ ዓለም አቀፍ ስታዲየም ግንባታ ዛሬ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ክቡር አቶ ጥላሁን ከበደ፣ በባህልና ስፖርት ሚኒስትር ወ/ሮ ሸዊት ሻንካ እና በወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ረዳት ፕሮፌሰር ሳሙኤል ተሰማ አማካኝነት የመሰረት ድንጋይ ተቀምጦለታል።
የስታዲየሙ ገፅታዎች:
✅ ደረጃ: የፊፋ (FIFA) እና የካፍ (CAF) ስታንዳርድን ያሟላ።
✅ አቅም: ከ40,000 እስከ 45,000 በላይ ተመልካቾችን የመያዝ አቅም አለው።
✅ ዲዛይን: የወላይታን ህዝብ ታሪክ፣ ባህላዊ እሴቶች እና የአካባቢውን ገፅታ ያካተተ ነው።
✅ ይዞታ: በ51 ሄክታር መሬት ላይ የሚያርፍ ይሆናል።
ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ፤ "ይህ ፕሮጀክት የህዝብ ነው፤ ከተባበርንና ካስተባበርን እውን ማድረግ ይቻላል" በማለት፤ የክልሉ መንግስት ለፕሮጀክቱ የሚሆን ልዩ የገቢ ማሰባሰቢያ መርሃ ግብር እንደሚያዘጋጅ ገልጸዋል።
የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ ረዳት ፕሮፌሰር ሳሙኤል ተሰማ በበኩላቸው፤ "እንደጀመርነው እንጨርሰዋለን!" በማለት መላው ህዝብ አሻራውን እንዲያሳርፍ ጥሪ አቅርበዋል።
ዎጌታ ኤፍ ኤም 96.6
#wolaita #stadium #construction #ethiopia
#wolaitasodo #internationalstadium #ethiopia #development #sports #southethiopia
5 months ago
"አንድ እንጀራ ለአንዲት እናት"
በጎ አድራጎት ማህበር የተፈናቀሉ እናቶችን ማዕድ አጋራ
• ከ200,000 ብር በላይ በሆነ ወጪ ድጋፍ ተደረገ
#ethiopia | "አንድ እንጀራ ለአንዲት እናት" በጎ አድራጎት ማህበር፤ በካዎ ኮይሻ ወረዳ በተፈጥሮ አደጋ ምክንያት ተፈናቅለው በአበላ አባያ ወረዳ ሰፍረው ለሚገኙ አቅመ ደካማ እናቶች እስከ መኖሪያ ስፍራቸው ድረስ በመጓዝ የምግብ እና የቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ።
ማህበሩ ከ201,000 (ሁለት መቶ አንድ ሺህ) ብር በላይ ወጪ በማድረግ የገዛውን ዘይት እና ዱቄት የወላይታ ዞን ዋና አስተዳደር ረዳት ፕሮፌሰር ሳሙኤል ተሰማ እና ሌሎች የዞኑ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች በተገኙበት በይፋ አስረክቧል።
የኃላፊዎች መልዕክት፡-
👤 ረዳት ፕሮፌሰር ሳሙኤል ተሰማ (የወላይታ ዞን ዋና አስተዳደር)፦
በዚህ በጎ ተግባር ላይ ለተሳተፉ አካላት ምስጋና ያቀረቡ ሲሆን፤ "እንደዚህ ዓይነት በጎ ተግባራት በዞኑ ውስጥ በሚሰሩ ማህበራትና ግለሰቦች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ የመንግስት ድጋፍና ክትትል አይለያቸውም" ብለዋል።
👤 ወጣት ስንታየሁ ሾላቶ (የማህበሩ ሰብሳቢ)፦
ማህበሩ ድንበር የሌለው እና ሰብዓዊነትን ብቻ መሠረት አድርጎ የሚሰራ መሆኑን ገልጸዋል። "ከትንሽ የበጎ ተግባራት ተነስቶ በሕዝቡ ዘንድ ተወዳጅነት እያተረፈ ወደዚህ ደረጃ ደርሷል" ያሉት ሰብሳቢው፤ በቀጣይም ከተለያዩ በጎ ፈቃደኞች ጋር በመተባበር ሰፊ እና ተጽእኖ ፈጣሪ ስራዎችን ለመስራት ማቀዳቸውን ተናግረዋል።
በጎነት ለራስ ነው!
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#wolaita #charity #andenjeraleanditenat #humanity #abelaabaya #ethiopia
በጎ አድራጎት ማህበር የተፈናቀሉ እናቶችን ማዕድ አጋራ
• ከ200,000 ብር በላይ በሆነ ወጪ ድጋፍ ተደረገ
#ethiopia | "አንድ እንጀራ ለአንዲት እናት" በጎ አድራጎት ማህበር፤ በካዎ ኮይሻ ወረዳ በተፈጥሮ አደጋ ምክንያት ተፈናቅለው በአበላ አባያ ወረዳ ሰፍረው ለሚገኙ አቅመ ደካማ እናቶች እስከ መኖሪያ ስፍራቸው ድረስ በመጓዝ የምግብ እና የቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ።
ማህበሩ ከ201,000 (ሁለት መቶ አንድ ሺህ) ብር በላይ ወጪ በማድረግ የገዛውን ዘይት እና ዱቄት የወላይታ ዞን ዋና አስተዳደር ረዳት ፕሮፌሰር ሳሙኤል ተሰማ እና ሌሎች የዞኑ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች በተገኙበት በይፋ አስረክቧል።
የኃላፊዎች መልዕክት፡-
👤 ረዳት ፕሮፌሰር ሳሙኤል ተሰማ (የወላይታ ዞን ዋና አስተዳደር)፦
በዚህ በጎ ተግባር ላይ ለተሳተፉ አካላት ምስጋና ያቀረቡ ሲሆን፤ "እንደዚህ ዓይነት በጎ ተግባራት በዞኑ ውስጥ በሚሰሩ ማህበራትና ግለሰቦች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ የመንግስት ድጋፍና ክትትል አይለያቸውም" ብለዋል።
👤 ወጣት ስንታየሁ ሾላቶ (የማህበሩ ሰብሳቢ)፦
ማህበሩ ድንበር የሌለው እና ሰብዓዊነትን ብቻ መሠረት አድርጎ የሚሰራ መሆኑን ገልጸዋል። "ከትንሽ የበጎ ተግባራት ተነስቶ በሕዝቡ ዘንድ ተወዳጅነት እያተረፈ ወደዚህ ደረጃ ደርሷል" ያሉት ሰብሳቢው፤ በቀጣይም ከተለያዩ በጎ ፈቃደኞች ጋር በመተባበር ሰፊ እና ተጽእኖ ፈጣሪ ስራዎችን ለመስራት ማቀዳቸውን ተናግረዋል።
በጎነት ለራስ ነው!
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#wolaita #charity #andenjeraleanditenat #humanity #abelaabaya #ethiopia
10 months ago
10 ሺህ ዜጎችን ተደራሽ የሚያደርገው ነጻ የሕክምና አገልግሎት
#ethiopia | በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ኮምፕሪሄንሲቭ እስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ለ1 ሳምንት የሚቆይ የነጻ ሕክምና አገልግሎት እየተሰጠ ነው፡፡
ነጻ የሕክምና አገልግሎቱ የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት አካል ሲሆን ለ10 ሺህ ዜጎች ተደራሽ እንደሚሆን የሆስፒታሉ የጤና ሳይንስና ሕክምና ኮሌጅ ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬክተር ዶ/ር ወኪል ወልዴ ገልጸዋል፡፡
ሆስፒታሉ ይህንን አገልግሎት ለመስጠት በተዘጋጀበት ወቅት ባለፈው ወር ድንገተኛ የእሳት አደጋ መከሰቱን ያስታወሱት ዶ/ር ወኪል ፤ በፈተናም ውስጥ ቢሆን ዕቅዱን ተግባራዊ ማድረግ መቻሉን ነው የተናገሩት።
በጎ ፈቃደነኛ ሐኪሞችን ጨምሮ መደበኛ ሐኪሞች ከሥራ ሰዓት ውጪ ይህንን ሥራ እንደሚደግፉም አስታውቀዋል።
አገልግሎቱን ከበጎ ፈቃደኛ ሀኪሞች ጋር በቅንጅት መስጠት መቻሉ የዘንድሮውን መርሐ-ግብር ለየት እንደሚያደርገውም ነው አክለው የገለጹት።
የራዲዮ ኢትዮጵያ ግብረሰናይ ድርጅት መስራች ዶ/ር ልሳነወርቅ ሆንሴቦ በበኩላቸው ይህ ሥራ 14ኛ የዘመቻ ተግባር መሆኑን ገልጸው፤ በአንድ ሳምንት ቆይታ ለ10 ሺህ ሰዎች ነጻ ምርመራና የሕክምና አገልግሎት ለመስጠት ዝግጅት ተደርጓል ብለዋል።
ስፔሻሊስቶችን ጨምሮ 15 የሕክምና ባለሙያዎች በነጻ አገልግሎቱ ተሳታፊ እንደሚሆኑም ጠቅሰዋል።
የአገልግሎቱ ተጠቃሚዎች በሰጡት አስተያየት ሕክምናው ወጪ እና ጊዜ የሚቆጥብ ከመሆኑ ባሻገር፣ የጤና ሁኔታቸውን ለይተው እንዲያውቁ ምቹ ሁኔታ እንደፈጠረላቸው ተናግረዋል።
በተመስገን ተስፋዬ
#ebc #freemedicalservice #wolaita
#ethiopia | በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ኮምፕሪሄንሲቭ እስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ለ1 ሳምንት የሚቆይ የነጻ ሕክምና አገልግሎት እየተሰጠ ነው፡፡
ነጻ የሕክምና አገልግሎቱ የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት አካል ሲሆን ለ10 ሺህ ዜጎች ተደራሽ እንደሚሆን የሆስፒታሉ የጤና ሳይንስና ሕክምና ኮሌጅ ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬክተር ዶ/ር ወኪል ወልዴ ገልጸዋል፡፡
ሆስፒታሉ ይህንን አገልግሎት ለመስጠት በተዘጋጀበት ወቅት ባለፈው ወር ድንገተኛ የእሳት አደጋ መከሰቱን ያስታወሱት ዶ/ር ወኪል ፤ በፈተናም ውስጥ ቢሆን ዕቅዱን ተግባራዊ ማድረግ መቻሉን ነው የተናገሩት።
በጎ ፈቃደነኛ ሐኪሞችን ጨምሮ መደበኛ ሐኪሞች ከሥራ ሰዓት ውጪ ይህንን ሥራ እንደሚደግፉም አስታውቀዋል።
አገልግሎቱን ከበጎ ፈቃደኛ ሀኪሞች ጋር በቅንጅት መስጠት መቻሉ የዘንድሮውን መርሐ-ግብር ለየት እንደሚያደርገውም ነው አክለው የገለጹት።
የራዲዮ ኢትዮጵያ ግብረሰናይ ድርጅት መስራች ዶ/ር ልሳነወርቅ ሆንሴቦ በበኩላቸው ይህ ሥራ 14ኛ የዘመቻ ተግባር መሆኑን ገልጸው፤ በአንድ ሳምንት ቆይታ ለ10 ሺህ ሰዎች ነጻ ምርመራና የሕክምና አገልግሎት ለመስጠት ዝግጅት ተደርጓል ብለዋል።
ስፔሻሊስቶችን ጨምሮ 15 የሕክምና ባለሙያዎች በነጻ አገልግሎቱ ተሳታፊ እንደሚሆኑም ጠቅሰዋል።
የአገልግሎቱ ተጠቃሚዎች በሰጡት አስተያየት ሕክምናው ወጪ እና ጊዜ የሚቆጥብ ከመሆኑ ባሻገር፣ የጤና ሁኔታቸውን ለይተው እንዲያውቁ ምቹ ሁኔታ እንደፈጠረላቸው ተናግረዋል።
በተመስገን ተስፋዬ
#ebc #freemedicalservice #wolaita
Sponsored by
Surafel
Comments