በአሰቃቂ የትራፊክ አደጋ የ11 ሰዎች ሕይወት አለፈ
#ethiopia | ከአልቾ ውሪሮ ወረዳ 18 ተጓዦችን አሳፍሮ በጠረጋ ከተማ በኩል ወደ ዋና ከተማዋ አዲስ አበባ በመጓዝ ላይ የነበረ አንድ አነስተኛ የህዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪ ከሰዓታት በፊት ከመስመር ውጭ በመውጣት ወደ ገደል ወድቋል።
በዚህ አሰቃቂ አደጋም በሰው ህይወትና በንብረት ላይ ከፍተኛ ውድመት ደርሷል።
በደረሰው አደጋ ምክንያት እናቶች፣ ህጻናት፣ ወጣቶችና አባቶችን ያካተቱ 11 ተጓዦች ህይወታቸውን ያጡ ሲሆን፣ ከአሽከርካሪ ጋር ሌላ ሁለት ሰዎች በድምሩ ሦስት ግለሰቦች ላይ ከባድ የአካል ጉዳት ደርሶ የህክምና እርዳታ እየተደረገላቸው ይገኛል።
በአንጻሩ ሁለት ህጻናትን ጨምሮ አራት ተጓዦች ከአደጋው ምንም አይነት ጉዳት ሳይደርስባቸው በሰላም ለመትረፍ ችለዋል።
የአልቾ ውሪሮ ወረዳ አስተዳደር በአደጋው ህይወታቸውን ያጡትን ወገኖች አስክሬን ከቡታጀራ ሆስፒታል ወደ ወራቤ ኮምፕሬሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል በማጓጓዝ ለቤተሰቦቻቸው የማስረከብ ስራ እየሰራ መሆኑን አስታውቋል።
በተመሳሳይ ሁኔታ ከባድ ጉዳት የደረሰባቸው ወገኖች በቡታጀራ እና በወራቤ ሆስፒታሎች ተገቢውን የህክምና ክትትል እንዲያገኙ በማድረግ ላይ ይገኛል።
#trafficaccident #roadsafe #ethiopianews #wolaita #butajira #worabe #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | ከአልቾ ውሪሮ ወረዳ 18 ተጓዦችን አሳፍሮ በጠረጋ ከተማ በኩል ወደ ዋና ከተማዋ አዲስ አበባ በመጓዝ ላይ የነበረ አንድ አነስተኛ የህዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪ ከሰዓታት በፊት ከመስመር ውጭ በመውጣት ወደ ገደል ወድቋል።
በዚህ አሰቃቂ አደጋም በሰው ህይወትና በንብረት ላይ ከፍተኛ ውድመት ደርሷል።
በደረሰው አደጋ ምክንያት እናቶች፣ ህጻናት፣ ወጣቶችና አባቶችን ያካተቱ 11 ተጓዦች ህይወታቸውን ያጡ ሲሆን፣ ከአሽከርካሪ ጋር ሌላ ሁለት ሰዎች በድምሩ ሦስት ግለሰቦች ላይ ከባድ የአካል ጉዳት ደርሶ የህክምና እርዳታ እየተደረገላቸው ይገኛል።
በአንጻሩ ሁለት ህጻናትን ጨምሮ አራት ተጓዦች ከአደጋው ምንም አይነት ጉዳት ሳይደርስባቸው በሰላም ለመትረፍ ችለዋል።
የአልቾ ውሪሮ ወረዳ አስተዳደር በአደጋው ህይወታቸውን ያጡትን ወገኖች አስክሬን ከቡታጀራ ሆስፒታል ወደ ወራቤ ኮምፕሬሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል በማጓጓዝ ለቤተሰቦቻቸው የማስረከብ ስራ እየሰራ መሆኑን አስታውቋል።
በተመሳሳይ ሁኔታ ከባድ ጉዳት የደረሰባቸው ወገኖች በቡታጀራ እና በወራቤ ሆስፒታሎች ተገቢውን የህክምና ክትትል እንዲያገኙ በማድረግ ላይ ይገኛል።
#trafficaccident #roadsafe #ethiopianews #wolaita #butajira #worabe #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
7 days ago