2 months ago
"ለሊቱን ሙሉ ስጸልይ ነው የማድረው ጸሎቱ አያስተኛኝም" እማማ ዝናሽ
አዎ አንተኛ ይሆናል "ጸሎቱም አያስተኛንም" ግን ምን ይሆን ጸሎታችን ?
የሌሊቱ "ቅዱስ" ውጊያ
እማማ ዝናሽ "ለሊቱን ሙሉ ስጸልይ ነው የማድረው" ሲሉ፣ እኛ ሰፈር ያሉት እትዬ አስቴርም ሌልቱን ሙሉ በጸሎት እንደሚያሳልፉ ይገልጻሉ። ባለፈው ሳምንት እርሳቸውም ለሊት ላይ አልጋቸው ላይ ቁጭ ብለው "ጸሎት" ጀመሩ አሉ ያው አሉ ነው እንግዴ...
ነገር ግን የእርሳቸው ጸሎት በግድግዳ ከሚዋሰናቸው ጎረቤት ጋር የሚደረግ ''ቅዱስ'' ውጊያ ነው።
"አቤቱ ፈጣሪ ሆይ... ይሄ ሰውዬ እንዳያነኮራፋ ወይ ልሳኑን ዝጋው አልያ ጆሮዬን እስከወዳኛው ድፈንልኝ ... ካልሆነ ግን የኮንደሚኒየም እጣ ይድረሰኝ እና ከዚህ ሰፈር ውልቅ አርገኝ"
ብዙዎቻችን እማማ ዝናሽ እንዳሉት "ለሊቱን ሙሉ ስጸልይ አድራለሁ" ስንል፣ ጸሎታችን መጽሐፍ ቅዱሳዊ ሳይሆን፣ የዕለት ተዕለት የኑሮ ሂሳብ ማወራረጃ ነው።
ለሊት 8 ሰዓት ላይ አይን ፍጥጥ ሲል የሚመጡት "ጸሎቶች" እንዲህ አይነቶቹ ናቸው፡-
"ፈጣሪ ሆይ፣ ያ የዛሬ ሦስት ዓመት የተበደርኩት ሰውዬ ነገ መንገድ ላይ እንዳያገኘኝ ሰውረው።"
"እባክህ ጌታ ሆይ፣ ነገ ጠዋት የምነሳበትን አላርም ስሰማ 'አምስት ደቂቃ ብቻ' ብዬ ተኝቼ ከአለቃዬ እንዳልናከስ መብረቅ አውርድና ቀስቅሰኝ አልያ እሱ ላይ ከባድ እንቅልፍ ጣልበት"
"አቤቱ... ትርሲት የፍቅር ጥያቄዬን ትመልስ አልያ ባለፈው ወክ ስንበላ ለብርድ ብዬ የሰጠኋትን ጃኬት ታምጣ!"
ይህንን ሁሉ ስታወጣና ስታወርድ ሌሊቱ ያልቃል፤ እማማ ዝናሽ እንዳሉት "ጸሎቱ አያስተኛንም!"
ሌሊት ላይ የሚደረግ ጸሎት ሌላው ባህሪው ሰውን "ሚሊየነር" ማድረጉ ነው። በአእምሮህ ውስጥ አዳዲስ ቢዝነሶችን ትጀምራለህ፣ ታተርፋለህ፣ ገቢዎች የሉም።
ነገር ግን ልክ ጠዋት 12 ሰዓት ሲልና ወፎቹ መጮህ ሲጀምሩ፣ ያ ሁሉ የሌሊት እቅድ እንደ ጉም በኖ ይጠፋል።በጸሎት የደከሙ አይኖቻችን ሙሉ ቀን በእንቅልፍ ሲያዳፉን ይውላሉ።
ፈጣሪ የእማማ ዝናሽን ጸሎት ይስማ፤
ቁጭ ብለው አድረዋልና...
በያፌት ገ/ህይወት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
አዎ አንተኛ ይሆናል "ጸሎቱም አያስተኛንም" ግን ምን ይሆን ጸሎታችን ?
የሌሊቱ "ቅዱስ" ውጊያ
እማማ ዝናሽ "ለሊቱን ሙሉ ስጸልይ ነው የማድረው" ሲሉ፣ እኛ ሰፈር ያሉት እትዬ አስቴርም ሌልቱን ሙሉ በጸሎት እንደሚያሳልፉ ይገልጻሉ። ባለፈው ሳምንት እርሳቸውም ለሊት ላይ አልጋቸው ላይ ቁጭ ብለው "ጸሎት" ጀመሩ አሉ ያው አሉ ነው እንግዴ...
ነገር ግን የእርሳቸው ጸሎት በግድግዳ ከሚዋሰናቸው ጎረቤት ጋር የሚደረግ ''ቅዱስ'' ውጊያ ነው።
"አቤቱ ፈጣሪ ሆይ... ይሄ ሰውዬ እንዳያነኮራፋ ወይ ልሳኑን ዝጋው አልያ ጆሮዬን እስከወዳኛው ድፈንልኝ ... ካልሆነ ግን የኮንደሚኒየም እጣ ይድረሰኝ እና ከዚህ ሰፈር ውልቅ አርገኝ"
ብዙዎቻችን እማማ ዝናሽ እንዳሉት "ለሊቱን ሙሉ ስጸልይ አድራለሁ" ስንል፣ ጸሎታችን መጽሐፍ ቅዱሳዊ ሳይሆን፣ የዕለት ተዕለት የኑሮ ሂሳብ ማወራረጃ ነው።
ለሊት 8 ሰዓት ላይ አይን ፍጥጥ ሲል የሚመጡት "ጸሎቶች" እንዲህ አይነቶቹ ናቸው፡-
"ፈጣሪ ሆይ፣ ያ የዛሬ ሦስት ዓመት የተበደርኩት ሰውዬ ነገ መንገድ ላይ እንዳያገኘኝ ሰውረው።"
"እባክህ ጌታ ሆይ፣ ነገ ጠዋት የምነሳበትን አላርም ስሰማ 'አምስት ደቂቃ ብቻ' ብዬ ተኝቼ ከአለቃዬ እንዳልናከስ መብረቅ አውርድና ቀስቅሰኝ አልያ እሱ ላይ ከባድ እንቅልፍ ጣልበት"
"አቤቱ... ትርሲት የፍቅር ጥያቄዬን ትመልስ አልያ ባለፈው ወክ ስንበላ ለብርድ ብዬ የሰጠኋትን ጃኬት ታምጣ!"
ይህንን ሁሉ ስታወጣና ስታወርድ ሌሊቱ ያልቃል፤ እማማ ዝናሽ እንዳሉት "ጸሎቱ አያስተኛንም!"
ሌሊት ላይ የሚደረግ ጸሎት ሌላው ባህሪው ሰውን "ሚሊየነር" ማድረጉ ነው። በአእምሮህ ውስጥ አዳዲስ ቢዝነሶችን ትጀምራለህ፣ ታተርፋለህ፣ ገቢዎች የሉም።
ነገር ግን ልክ ጠዋት 12 ሰዓት ሲልና ወፎቹ መጮህ ሲጀምሩ፣ ያ ሁሉ የሌሊት እቅድ እንደ ጉም በኖ ይጠፋል።በጸሎት የደከሙ አይኖቻችን ሙሉ ቀን በእንቅልፍ ሲያዳፉን ይውላሉ።
ፈጣሪ የእማማ ዝናሽን ጸሎት ይስማ፤
ቁጭ ብለው አድረዋልና...
በያፌት ገ/ህይወት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
3 months ago
"በኢትዮጵያ ሰማይ ላይ
የሚበራው የሙዚቃ ኮከብ "
ከአለባቸው ደሳለኝ አበሻ (ለንደን)
#ethiopia | "ድምፁ የሀገር ሰንደቅ ዓላማ ያህል ክብር የሚሰጠው ጥላሁን ገሰሰ ለግማሽ ክፍለ ዘመን ያህል በኢትዮጵያ ሙዚቃ ውስጥ በነበረው ከፍተኛ አስተዋፅኦ የኢትዮጵያ ሙዚቃ ንጉሥ በሚል መጠሪያ ይታወቃል።
ለዚህ የጥበብ ሰው እንዲህ ያለ ጥልቅ እና ልብ የሚነካ ትዝታ ማዘጋጄት የሚቻለው የጥላሁን ገሰሰን ስራዎችን ብቻ ሳይሆን የእርሱን የውስጥ ማንነት ሠብዕናን ለጥበብ የነበረውን ፍቅር በሚገባ የተረዳ መሆን አለበት ።
ወይንም ደግሞ
የዚህን ታላቅ ምትሐተኛ ድምፃዊ የጥበብ ልክና የድምፅ ብቃት በአግባቡ ለመረዳት የእርሱን ግለ ታሪክ ብቻ ሳይሆን የኢትዮጵያን ዘመናዊ ሙዚቃ ታሪክና የጥላሁን ገሰሰን ሰፊ የሥራ ክምችቶች በጥልቀት መመርመር የግድ ይላል።
ምክኒያቱም
ጥላሁን ገሰሰ ማለት የኢትዮጵያ የ50 ዓመታት የደስታ የሐዘን የድልና የሽንፈት ታሪክ በድምፅ የተቀረጸበት "ሕያው ማህደር" ነው።
ጥላሁን ገሰሰ ድምፁን እንደፈለገ የማዘዝ Vocal Control ልዩ ተሰጥኦ ነበረው።
በጣም ረጅምና ከፍተኛ ድምፅ በሚጠይቁ High notes እንዲሁም በጣም ረጋ ያሉና ዝቅተኛ ድምፅ በሚሹ Low notes ዜማዎች ላይ እኩል ብቃት ነበረው።
የትንፋሽ ቁጥጥሩ ረጅም ስንኞችን ሳያቋርጥና ትንፋሽ ሳይጠረው የመጨረስ ችሎታው የሚደነቅ ነበር።
የጥላሁንን ስራዎች ስንመረምር በአንድ የሙዚቃ ዘውግ ብቻ ያልተገደበ መሆኑን እንረዳለን
ባህላዊና ዘመናዊ የባህል ሙዚቃዎችን ከዘመናዊ መሣሪያዎች ኦርኬስትራ ጋር አዋህዶ በማቅረብ ረገድ ቀዳሚ ነበር።
በጥላሁን ገሠሠ ድምፅ ያልተዘፈነ የሕይወት ክፍል የለም ማለት ይቻላል ።
ከጥልቅ የፍቅር ስሜት እስከ ሃገር ፍቅር ከማህበራዊ ትችት እስከ መንፈሳዊ መዝሙራት ድረስ የተፃፉ ግጥሞችና ዜማዎች የጥላሁንን ገሠሠን ድምፅ ለማድመቅ ሳይሆን ለመፈተን ጭምር የተዘጋጁ ይመስሉ ነበር።
በህይወት በቆየባቸው ሦስት የተለያዩ ሥርዓቶች በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ በደርግና በኢህአዴግ ውስጥ አልፏል። በእነዚህ ሁሉ ጊዜያት የሕዝብ ተወዳጅነቱን ጠብቆ መቆየቱ የሙዚቃ ሥራዎቹ ከፖለቲካዊ ለውጦች በላይ የሕዝብን የልብ ትርታ የሚነኩ መሆናቸውን ያሳያል።
ባጭሩ ጥላሁን ገሰሰ ለኢትዮጵያ ሙዚቃ ያለው አስተዋጽኦ ልክ እንደ አንድ ትልቅ "ኢንሳይክሎፒዲያ" ነው። አንዱን ገጽ አንብቦ ስለ መጽሐፉ ሙሉ ግንዛቤ ማግኘት እንደማይቻል ሁሉ
አንዱን ዘፈን አዳምጦ ስለ ጥላሁን ገሰሰ ማወቅ አይቻልም ።
እያንዳንዱ ዘፈኑ የራሱ የሆነ የቴክኒክ የታሪክና የስሜት ጥልቀት አለው።
ስለዚህ የጥላሁንን ታላቅነት ለመረዳት የኢትዮጵያን የሙዚቃ ጉዞ አብሮ መመርመር የግድ ነው ያልኩት ወድጄ አይደለም ።
ዘፈኖቹን ሲዘፍን በቃላት ብቻ ሳይሆን በፊቱ መግለጫና በሰውነት እንቅስቃሴው Body Language ጭምር ስሜቱን ለታዳሚው ያጋባ ነበር።
በተለይ የሐዘን ዜማዎችን ሲዘፍን አብሮ የሚያለቅስ የደስታ ሲሆን ደግሞ አብሮ ፈገግ የሚል ድምፃዊ ተዋና ጭምር ነበረ በዘፈኖቹ ውስጥ ሰውን ማክበርን ስራን መውደድንና አንድነትን ይሰብካል። ዘፈኑ የሰውን ልጅ ክብርና ማንነት የሚተነትን ድንቅ ስራ የሚሰራ ምትሀተኛ ድምፃዊ ነበር ።
ጥላሁን ገሰሰ በአንድ ወቅት በመድረክ ላይ እያለ በደረሰበት የጉሮሮ ህመም ምክንያት ለተወሰነ ጊዜ ድምፁ ተዘግቶ ነበር። ያን ጊዜ መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ተጨንቆና ፀልዮ ድምፁ ሲመለስለት ያደረገው የመጀመሪያ ኮንሰርት በዚያን ወቅት በኢትዮጵያ የሙዚቃ ታሪክ ውስጥ ከፍተኛውን የሰው ቁጥር ያስመዘገበ ነበር ። ይህ የሚያሳየው ሕዝቡ ለጥላሁን ያለው ፍቅር ከአንድ ድምፃዊ በላይ እንደ ቤተሰብ አባል የሚያየው መሆኑን ነው።
ስለ ፍቅር ብቻ ሳይሆን ስለ ሰው ልጅ ሕይወት ባዶነት የሚተርክ ጥልቅ ፍልስፍና ነበረው ።
ታዋቂው የኢትዮጵያ የሙዚቃ ንጉሥ ክቡር ዶክተር ጥላሁን ገሰሰ መስከረም 17 ቀን 1933 ዓ.ም አዲስ አበባ ውስጥ ተወልዶ ያደገው ግን በወሊሶ ከተማ ነው ።
ጥላሁን በ1950ዎቹ መጀመሪያ ላይ ወደ አዲስ አበባ በመምጣት መጀመሪያ ሐገር ፍቅር ቲያትርን በኋላም ዝነኛውን የክብር ዘበኛ የሙዚቃ ቡድንን ተቀላቅሎ ከዕንስት ፍቅር እስከ አገር ፍቅር ከባህላዊ እስከ ዘመናዊ ሙዚቃ በድምፃዊነት ከ400 በላይ ዘፈኖችን ተጫውቶ ልዩ ብቃቱን አስመስክሯል ።
ጥላሁን
ለኢትዮጵያ ሙዚቃ ላበረከተው ወደር የለሽ አስተዋጽኦ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የክብር ዶክትሬት ዲግሪ ተሰጥቶታል። ጥላሁን ገሠሠ ከዚህ ዓለም በሞት የተለየው
በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር ሚያዝያ 11 ቀን 2001 ዓ.ም. የፋሲካ እለት ሲሆን በድንገተኛ የልብ ህመም ምክንያት አርፎ በቅድስት ሥላሴ ካቴድራል የቀብር ሥነሥርዓቱ ተፈጽሟል።
የክቡር ዶክተር ጥላሁን ገሰሰ ማረፍ መላውን የኢትዮጵያ ሕዝብና የጥበብ አፍቃሪወችን በከፍተኛ ድንጋጤና ሃዘን ውስጥ ጥሎ የነበረ ክስተት ነው። በወቅቱ በጋዜጦች በሬዲዮና በቴሌቪዥን የተላለፉት መልዕክቶች ጥላሁን ለሀገሩ ያለውን ትልቅ ቦታ የሚያንፀባርቁ ነበሩ።
በአዲስ አበባ ከተማ የነበሩ የታክሲ አሽከርካሪዎች ሐዘን ፈፅሞ የማይረሳ ነበረ ።
ለጥላሁን ገሰሰ ክብር ሲሉ ለቀናት ጥቁር ጨርቅ በታክሲዎቻቸው ላይ አስረውና የእርሱን ሙዚቃ ብቻ ከፍተው በማጫወት ሃዘናቸውን ገልፀውለታል።
የጥላሁን ገሰሰ ሞት በሀገር ውስጥ ብቻ ሳይሆን በዓለም አቀፍ ደረጃም ትኩረት አግኝቶ ነበር።
ታዋቂው ደራሲ ሎሬት ጸጋዬ ገብረመድህንም
እንዲህ አሉ ።
"ጥላሁን የኢትዮጵያ ሕዝብ የጋራ ድምፅ ነው። እርሱ ሲዘፍን መላው ኢትዮጵያዊ ራሱን ያዳምጣል።"
ድምፃዊ ማህሙድ አህመድ"ጥላሁን ለእኛ ለድምፃውያን መምህራችን ብቻ ሳይሆን የሙዚቃው ዓምድ ነበር። ጥላሁን ሞተ ማለት የኢትዮጵያ ሙዚቃ ግማሽ አካሉን አጣ ማለት ነው።" ሲል ቁጭቱን ገልፀዋል ።
በቀብር ሥነ ሥርዓቱ ላይ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ አዲስ አበባውያን ወደ አደባባይ በመውጣት "ንጉሥ አይሞትም" እያሉ ሲያለቅሱ እንደነበር በታሪክ ተመዝግቧል።
ይህም አንድ ድምፃዊ በሀገር ደረጃ ያለውን ክብርና ተሰሚነት ያሳየ ትልቅ ክስተት ነበር።
አንድ የልብ አድናቂው የሆነ ሠው በማህበራዊ ሚዲያ እንዲህ ብሎ ፅፎት አንብቢያለሁ ።
" በእርግጥም ጥላሁን በድምፁ ተአምር የመስራት አቅም ነበረው። ድምፁ ተስፋ የቆረጠውን የሚያፅናና የታመመውን የሚፈውስና የራቀውን የሚያቀራርብ
ስለነበረ ድምፁ ተቀርፆ ስለቀረ ቢሞትም ስንናፍቀው እናገኘዋለን ስናዝን እናለቅስበታለን ሀገራችን ስትጠራ በእሱ ድምፅ አቤት ብለን ለአንድነቷ እንቆማለን" በማለት ጥላሁንን ገልፆት ነበር ።
ሌላው የቅርብ ጓደኛው የጥበብ ሰው ደበበ እሸቱ ነው
"ጥላሁን በሕይወት ዘመኑ ሁሉ ለሀገሩ የዘመረ በችግር ጊዜ ደግሞ ድምፁን ለድሆች የሰጠ
ታላቅ ሰው ነው።
የሞተው በስጋ ቢሆንም በዜማው ቅላፄና በግጥም ስንኞች ውስጥ "ዘላለማዊ" ሆኖ ተተክሏል።
እንዲህ ያለ ድምፅ ዓለማችን በአንድ ዘመን አንዴ ብቻ የምትለግሰን ስጦታ ነው "
ሲል ምስክርነቱን ገልጿል።
በእርግጥም ጥላሁን የዘመናዊ ሙዚቃችን "ፊደል" እና "መዝገበ ቃላት" ሆኖ አልፏል። ከድምፅ ጥራት በላይ የዜማ አጣጣልና ስሜትን የመግለጽ ጥበቡ ማንም የማይደረስበት ከፍታ ላይ ስለነበር በአንድ አባባል ብቻ ጥላሁንን መግለፅ አይቻልም።
እሱ ባለብዙ ምዕራፍና ተነቦ የማይጠገብ ባለ ብዙ ገጽ ድርሳን ነው !
ጥላሁን ለሙያው ብቻ ሳይሆን ለሰው ልጅ የነበረው ሰብአዊ ክብርም ድንቅ ነበር። ረሀብ ሲመጣ በዜማው የሚማፀን ሀገር ስትቸገር አጥንቴም ይከስከስ ብሎ የሚቆም እና ለሰው ልጅ ፍቅር ቅድሚያ የሚሰጥ የጥበብ ሰው ነው ። ባጭሩ ጥላሁን ገሠሠ ማለት ለኢትዮጵያውያን የድምፅ ብቻ ሳይሆን የህሊና ምስክር ነው።
ዛሬም ድረስ ስሙ ሲነሳ አብሮ የሚነሳው ክብሩ ትህትናውና
ያ የማይደገም ማንነቱ ነው።
ጥላሁን ገሠሠን የመሠለ ታላቅ ሰው የኢትዮጵያ ዘመናዊ ሙዚቃን የአዋለደ ብለን ብንገልፀው ተገቢ ይመስለኛል ከጥላሁን ገሠሠ ስራዎች መካከል ይህማ ተአምር ነው የሚያሰኜኘኝ ሁልጊዜ ብሰማቸው አዲስ የሚሆኑብኝ ብዙ ዘፈኖች ቢኖሩትም "እዩት ስትናፍቀኝ ከአጠገቤ እያለች" የሚለው ስንኝ ሲነሳ ግን የጥላሁንን ድምፅና ያንን የሚመስጥ አዘፋፈኑን አብሮ የመስማት ያህል ይመስጠኛል እዩት ስትናፍቀኝ ከአጠገቤ እያለች
እንዲህ ያለው መውደድ ለወሬም አይመች ! የሚለው ግጥም የፍቅርን ረቂቅነትና የማይመረመር ባህሪ በአጭር ቃላት የገለጸበት ድንቅ ስራው ነው።
ጥላሁን ለዚህ ዘፈን የሰጠው እረዥም ትንፋሽና በመድረክ ላይ ቆሞ የአይን አስተያየቱ የልዩ ተሰጥኦው መገለጫዎቹ ናቸው።
የሠው ልጅ ናፍቆት ብዙውን ጊዜ ትዝታው የሚመጣው ሰው ሲርቅ ነው። ነገር ግን ጥላሁን አጠገቤ እያለች ናፈቀችኝ ማለቱ ፍቅር ከስጋዊ መገኘት በላይ የሆነ የነፍስ ጥማት መሆኑን ስጋ አልብሶ አሳይቶናል ።
ይህ ለወሬ የማይመች ቃላት የማይገልፁት ጥልቅ ስሜት ነው ። ይህንንም በዚያ ረጅም ትንፋሽ ነፍስን በሚያከነፍ ድምፁ ሲያዜመው እውነቱን በውስጣችን ውስጥ እናገኘዋለን።
ጥላሁን ሲዘፍን ትንፋሹን የሚጠቀምበት መንገድ እና ስሜቱን በድምፅ ቀለም የመቀየር ችሎታው ምትሐተኛ ያሰኘዋል። ያንን የናፍቆት ጣጣ በገዛ ራሱ ላይ አድርጎ ሲያዜመው አድማጩ የራሱ ህመም አድርጎ እንዲቀበለው የማድረግ ልዩ ኃይል ነበረው።
ጥላሁን ገሠሠ በስጋ ቢለየንም በኢትዮጵያውያን ልብ ውስጥ ግን አሁንም ንጉሥ ነው።
ትውልድ ያልፋል ጥላሁን ግን ይኖራል።
ሙዚቃ ይቀየራል የጥላሁን ስራዎች ግን ሁልጊዜ አዲስ ናቸው።
ሰላም ሲጠፋ ጥላሁን ፍቅር ይላል ሀገር ስትናፈቅ ጥላሁን ሀገሬ ይላል።
ጥላሁን ገሠሠ በድምፁ ብቻ ሳይሆን ለፍቅር በሰጠው ክብርን በገለፀበት ጥበብ የኢትዮጵያ የዘላለም የፍቅር አምባሳደር ነው።
እንዲህ ያለው የጥበብ ሰው የፍቅርን ኃያልነት በእሱ ስራዎች ውስጥ ስንመለከት በእርግጥም ፍቅር ስሜት ብቻ አይደለም የሚለውን ሃሳብ በጥላሁን ዜማዎች ውስጥ ሙሉ ማረጋገጫውን እናገኛለን ጥላሁን ገሠሠ የፍቅርን ሌላኛውን ገጽታ ቁርጠኝነትንና ክብርን ያሳየበት ድንቅ ስራው ነው። ከላይ እንደገለፅኩት ፍቅር ራስን አሳልፎ መስጠት ነው
እዚህ ዘፈን ላይ ደግሞ ፍቅር ሁለትዮሽ መረዳዳት መሆኑን ይነግረናል።
ቻልኩት ፍቅር ለብቻዬ !!
ይህ አገላለጽ በጣም የሚቆረቁር ነው። ፍቅር እንደ አንድ ሸክም ሆኖ አንደኛው ወገን ብቻውን ሲሸከመው የሚሰማውን ድካም ያሳያል። "ለብቻዬ መሸከም ሰልችቶኛል" የሚል የልብ ጩኸት አለበት። ፍቅር የሁለት ሰው ቅኝት እንጂ የአንድ ሰው ብቸኛ ትግል መሆን እንደሌለበት ያስገነዝበናል።
ስለ ፍቅር አልገባሽም
እዚህ ጋር ጥላሁን ፍቅር ማለት ዝም ብሎ አብሮ መሆን ሳይሆን ጥልቅ የሆነ
ሚስጥር ወይም ትርጉም እንዳለው ይገልጻል። ግዴለሽነት እና ችላ ማለት ፍቅርን የሚገድሉ መርዞች መሆናቸውን በምሬት ይናገራል።
አትምጪ ይቅር ሲል ደግሞ የክብር ውሳኔውን ያሳውቃል ።
ፍቅር ስሜት ብቻ አለመሆኑን ያረጋግጣል። አንድ ሰው በጥልቅ እያፈቀረ ግን ክብሩ ሲነካ ወይም ምላሽ ሲያጣ ይቅር ብሎ የመወሰን አቅም ሊኖረው እንደሚገባ ያሳያል።
ፍቅር መስዋዕትነት ቢሆንም ዋጋ በማይሰጠው ቦታ ላይ ግን ራስን ማዳንና ይቅር ማለትም የፍቅር አካል ነው። የሚገርመው ደግሞ ጥላሁን ይህነን ዘፈን ሲዘፍነው በቁጣና በቁጭት ሳይሆን በጥልቅ ሀዘንና በከበረ ስሜት ነው። ያንን አትምጪ ይቅር የሚለውን ቃል ሲያወጣው ውስጡ እየፈለጋት ግን መከባበር የሌለበት ፍቅር እንደማይፀና አውቆ በቁርጠኝነት ሲናገረው ይታየናል።
ከላይ እንዳነሳሁት አትምጪ ይቅር የሚለው ስንኝ የቁርጠኝነትና የክብር ገጹ ሲሆን ሌላው ደግሞ የፍቅርን ንፁህ መስዋዕትነትና ትህትና የሚያሳይ ድንቅ ምዕራፍ ነው።
እነዚህ ስንኞች ውስጥ የምናያቸው የጥላሁን ድርሳናት
እኔ ልሁን እንጂ የማልጠቅም እርካሽ ! የሚለው አገላለፅ በፍቅር ውስጥ ያለን ፍጹም ትህትና ያሳያል። ራሱን ዝቅ አድርጎ የሚወዳትን ሰው ግን ከፍ ያደርጋታል። ይህ እኔነት ጠፍቶ አንቺነት የነገሰበት የፍቅር ጫፍ ነው።
ከህይወቴ አብልጨ ሲል
ራስን አሳልፎ የመስጠት
ፍልስፍና በተግባር የሚያሳይ ታአምር ነው። ለሰው ልጅ ከህይወቱ በላይ ምንም የለውም ነገር ግን ፍቅር ያንን ውድ ህይወት እንኳ ከአንቺ አያበልጠውም ብሎ እንዲያምን ያደርገዋል።
ፍቅር ለሰላምና ለደስታ ብቻ ሳይሆን ለችግርና ለፈተናም ዝግጁ መሆኑን ይነግረናል።
መከራና ስቃይ ይቆየኝ ግዴለኝም
የሚወደው ሰው ደህንነትና ሰላም እስካለ ድረስ እሱ በራሱ ላይ ለሚመጣው መከራ ግድ የለውም። ይህ ነው እንግዲህ ፍቅርን ተአምር የሚያሰኘው እግዜር በጥበቡ ከአንቺ ብቻ አይለየኝ የሚለው ቃል ፍቅር በሰው ጥረት ብቻ ሳይሆን በመለኮታዊ ጥበብና ፈቃድ የሚፀና መሆኑን የሚያሳይ የልብ ፆሎት በመሆኑ መንፈሳዊ ልመና ይጨምርበታል ።
ታዲያ የዚህን ድምፃዊ ተአምራዊ ተቃርኖዎችን ስንመለከት
ጥላሁንን ልዩ የሚያደርገው በአንድ በኩል አትምጪ ይቅር ብሎ በክብር የመወሰን አቅም በሌላ በኩል ደግሞ ከህይወቴ አብልጨ እወድሻለሁ ብሎ ራስን የመስጠት ርህራሄ አብሮት መኖሩ ነው።
እነዚህ ሁለት ተቃራኒ የሚመስሉ ግን ጥልቅ የሆኑ የፍቅር ገጾች ናቸው።
ጥላሁን እነዚህን ሁሉ ስሜቶች በድምፅ ቀለም እየቀያየረ ሲያቀርባቸው ድምፁ ብቻ ሳይሆን ነፍሱ አብራ የምትዘፍን ይመስላል።
እንዲህ ያለውን ከህይወት በላይ የመውደድ ስሜት በዚህ ዘመን በብዛት እናገኘዋለን ብሎ ማሰብ የዋህነት ነው። ምክኒያቱም
የጥላሁንን ጥበብ ከመዝፈን ባለፈ ወደ መፍጠር ደረጃ ከፍ ያደርገዋል።
ለምን ቢባል ጥላሁን ገሠሠ ዜማንና ግጥምን ሲያዋህድ የሚፈጠረው ነገር ተራ ሙዚቃ አይደለም ይልቁንም ያልተጠኑ ምስጢራዊ ተሰጥኦዎች ያሉበት ይመስላል
ብዙ አድናቂወቹ እንደ ሚስማሙበት ጥላሁን ገሠሠ ሲዘፍን ፍቅር ረቂቅ ሃሳብ መሆኑ ቀርቶ የሚዳሰስ የሚታይና የሚሰማ አካል ይኖረዋል።
ቃላቶቹ ከአፉ ሲወጡ ሕይወት ይዘራሉ ያፈቀረው ሰው ቁስሉ ይታየናል የናፈቀው ሰው ትንፋሹ ይሰማናል። ይህ ደግሞ በቴክኒክ ብቻ የሚመጣ ሳይሆን ከነፍስ የሚመነጭ ምትሃት በመሆኑ ፍቅር እንደ ሰው ቆሞ እንዲሄድ የማድረግ ጥልቅና ረቂቅ
ጥበብ ያለው ድምፃዊ መሆኑ ነው ።
ብዙዎቻችን ውስጣችን ያለውን ጥልቅ ፍቅር በቃላት መግለፅ ያቅተናል። ጥላሁን ግን ያንን መግለፅ ያቃተንን ስሜት ሰርቆ ወስዶ በዜማ አቅልጦ ወርቅ አርጎ መልሶ ለእኛው ይሰጠናል።
እኔንም እንዲህ ነው የሚሰማኝ! እንድንል ያደርገናል። ይህ ተሰጥኦው ነው ፍቅርን ስጋ ለብሶ ቆሞ እንዲሄድ የሚያደርገው።
ሌላው የጥላሁን ገሰሰ ድምፅ ሁለንተናዊ ድምፅ መሆኑ ነው። እድሜ ጾታ ወይም የትምህርት ደረጃ አይወስነውም። ህፃኑም አዋቂውም የተማረውም ያልተማረውም በዜማው ውስጥ የራሳቸውን ታሪክ ያገኛሉ።
ይህ ደግሞ ጥላሁን የሰው ልጅን የጋራ የፍቅር ህመም ጠንቅቆ እንደሚያውቅ ማሳያ ነው።
የጥላሁን ድምፅ በሳይንስ አልተጠናም እንጂ በውስጡ ትልቅ የፍቅር ላብራቶሪ ነበረው ማለት ይቻላል።
ግጥሙን ይቀበላል ጥሬ እቃ !
በድምፅ ቀለሙ ያዋህደዋል ሂደት !
በመጨረሻም ሕያው ፍቅርን ለዓለም ያበረክታል ውጤት !! በዚህ ምክኒያት
ጥላሁን ገሠሠ ሞቶም በሰዎች ልብ ውስጥ እንዲነግስ አድርጎታል :: ምክንያቱም የፈጠራቸው የፍቅር አካላት ዛሬም በየቤታችን በየመኪናችንና በየልባችን ውስጥ ቆመው እየሄዱ ነው።
ይህ የእውነት ተአምረኛ ተሰጥኦው ነው። ዛሬ ባለው ዘመናዊ የሙዚቃ ኢንዱስትሪ ውስጥ እንዲህ ያለውን መንፈሳዊ ጥልቅነት ማግኘት እጅግ ብርቅ ሆኗል። ከእንስት ፍቅር ወጥተን ጥላሁንን ወደ ሐገር ፍቅር ስንመነዝረው የቆመበት ከፍታው ላይ እስከ አሁን ማንም ....ማንም አልደረሠበት ። በዚህ አጋጣሚ
በህይወቴ ዘመኔ በአይኔ ያየሁትን ምስክርነት ባቀርበው ደስ ይለኛል ጥለሁን ገሠሠ ከታሪክ መዝገብ በላይ የሆነ የአንድን ሕዝብ ማንነትና ወኔ የቀሰቀሰ የመንፈስ ተአምር ነው የምነግራችሁ ።
ጊዜው 1974 አስመራ የቀይ ኮኮብ ዘመቻ አሉላ አባ ነጋ አዳራሽ ውስጥ ይመስለኛል ።
ጥላሁን ገሠሠ ጋሻና ጎራዴ ይዞ የአርበኛ ልብስ ለብሶ አጥንቴም ይከስከስ ደሜም ይፍሠስላት
ግን ሐገሬን ጭራሽ አይደፍራትም ጠላት
እያለ መድረኩን ሞልቶት ብቅ ሲል ከባለስልጣን እሰከ ተራው ተመልካች ከመቀመጫው ተነስቶ በመቆም በማያቋርጥ ጩህትና ጭብጨባ ያጅቡታል ።
ጥላሁን ገሠሠ በዚያ ቅጽበት የዘፈነውን ብቻ ሳይሆን የኖረውንና የታሪካችንን ድምፅ ሆኖ ተመለከትኩት ።
ጥላሁን በህዝብ ጭብጨባና ጬህት ታጅቦ መድረኩ ላይ ሲንጎራደድ አዳራሹ ድብልቅልቁ ወጣ ።
ያን... ምህታታት የተሞላበት ትርኢት ስመለከት
የአድዋ ጀግኖች መቃብር ከፍተው የተነሱ ይመስል ነበር።
ማለቴ ጥላሁን በድምፁ ብቻ ሳይሆን በቆይታው ጊዜን የማቆም ወይም ታሪክን የመቀስቀስ ኃይል እንደነበረው የመመልከት ዕድል አግኝቻለሁ ።
ጥላሁንን በዚያች ቅፅበት
በሕይወት እያለ ሐውልቱን አቁሞ አዳራሹ ውስጥ ታሪኩን ፅፎት ወጣ ።
በእርግጥ ሐውልት የማይናገርና የማይሰማ የድንጋይ ምስል ነው ጥላሁን ግን በሕይወት ያለ የሚተነፍስ የሚዘፍንና የሚራመድ የኢትዮጵያዊነት ሐውልት ነበር።
ዛሬም ቢሆን ስራዎቹ ያንን ግርማ ሞገስና ያንን ሐውልታዊ ፅናት እያስታወሱኝ እስከእለተ ሞቴ ድረስ ልረሳው አልችልም እንዲህ አይነት ድርጊት
ፍቅር ስሜት ብቻ አይደለም ራስን አሳልፎ መስጠት ነው በጥላሁን ገሰሰ የሀገር ፍቅር ዜማዎች ውስጥ ኢትዮጵያን ደጋግመን እናያታለን
አጥንቴም ይከስከስ ደሜም ይፍሰስላት የሚለው ቃል ዛሬም ድረስ ፍፁም ....ፍፁም መስዋዕትነት ነው።
ሀገሩን እንደ ሚወዳት እናት ወይም ሚስት አድርጎ ለሷ ክብር መሞትን እንደ ትልቅ ፀጋ መቁጠር ከፍ ያለ የፍቅር ደረጃ መግለጫ ነው።
ተመልካቹ በሙሉ ሳይቀመጥ ከሁለት ጊዜ በላይ ይደገም እያለ መጠየቁ ጥላሁን ድምፃዊ ብቻ ሳይሆን መሪ መሆኑን በአንድ ዜማ ሕዝብን የማስተሳሰር በአንድ ወኔ በጋራ የማቆም ተአምራዊ አቅሙን አረጋግጨበታለሁ ።
በዚያች ቅፅብት ቲያትር ቤቱ በጩሄትና በጭብጨባ ቀውጢ ሲሆን ጥላሁን ገሠሠ በድምፁ ብቻ የጠላትን ምሽግ የሚያፈርስ ጀግና መስሎ ነበር የሚታየው ።
ምንም እንኳን ዛሬ በሞት ቢለየንም ያ አስመራ ላይ የተመለከትኩት የሐገር ፍቅር ስሜት ሐውልት ሆኖ በልቤ ውስጥ ተቀርፆ ቆሟል።
ጥላሁን ገሰሰን ልዩ የሚደርገው ሌላው መገለጫው
ለፍቅር ሲዘፍን የፍቅር ሐውልት
ለሀገር ሲዘፍን የጀግንነት ሐውልት
ለሰው ልጅ ክብር ሲዘፍን የሰብአዊነት ሐውልት ነው!
ለዚህ ስኬት ደግሞ ከጥላሁን ድምፅ ጀርባ የነበሩት የወርቃማው ዘመን ታላላቅ የጥበብ ሰዎች ገጣሚያንና የዜማ አቀናባሪዎች ሚና ከፍተኛ እንደነበር ምስክሩ ታሪክና ሕዝቡ ነው።
ጥላሁን ገሰሰ ግጥምና ዜማን
ከነጄነራል አማኑኤል አብርሃም
ሻምበል አፈወርቅ ዮሐንስ
ነጋሽ ገብረማርያም
ተስፋዬ አበበ አየለ ማሞ ሳህሌ ደጋጎ ክፍሌ አቦቸር ከመሳሰሉት የክብር ዘበኛ እና የፖሊስ ኦርኬስትራዎች
ተቀብሎ ሲያንቆረቁረው ሙዚቃው ከድምፅ አልፎ የሚዳሰስ ሕያው መንፈስ የመሆን አቅም ነበረው።
ዛሬ ላይ ሆኜ ያንን ትርኢት ሳስታውሰው ጥላሁን ለኢትዮጵያ ሙዚቃና ለኢትዮጵያዊነት ያለው ትርጉም ምን ያህል ጥልቅ ስሜት እንደሆነ አሁን ድረስ እንደ ህልም ይታየኛል ።
ያኔ መድረክ ላይ ሲወጣ የነበረው ግርማ ሞገስና ድምፁ ሲስተጋባ የተሰማኝ ስሜት ዛሬም ድረስ ዘፈኑን ስሰማው "የጦር ፊታውራሪ" የነበረ ጀግና ያህል ትዝ ይለኛል !!
ጥላሁን በመድረክ ላይ የነበረውን የበላይነት እና የሕዝብን ስሜት የመምራት ብቃቱን በሚገባ የመግለፅ አቅም ነበረው ።
ጥላሁን ዝም ብሎ ድምፃዊ ሳይሆን በዜማው የታጠቀ የሀገር መከታ ወታደርም ሆኖ እንደነበረ ማሳያ ነው ።
ለዚህ ነው የጥላሁን ገሠሠ የሀገር ፍቅር ዜማዎች ከጊዜና ከቦታ በላይ የሆኑ ናቸው የሚባሉት ። ለዚህም ነው ዛሬ ላይ ሆነን ስንሰማው የዛሬ 130 ዓመት በፊት የተነገረውን የዳግማዊ ምኒልክን የክተት አዋጅ የሚመስለን ።
ይህ የሚያሳየው ደግሞ ጥላሁን የኢትዮጵያን ታሪክ ኩራትና ነፃነት በድምፅ ቀርጾ ትውልድ እንዲወርሰው ማድረጉን ነው።
ወዳጆቼ
ስለ ጥላሁን ገሠሠ የሀገር ፍቅር ስሜት ስንናገር እነዚህ ሶስት መሰረታዊ እውነታዎች ጎልተው ይታያኛል ።
የቁርጠኝነት ድምፁን ስናደዳምጠው ጥላሁን "አገሬን" ሲል ዝም ብሎ ስም አይጠራም ለሀገሩ የሚሞትላትና የሚሰዋላት መሆኑን በቃናው ውስጥ ይሰማል። አጥንቴም ይከስከስ የሚለው ስንኝ ለዚህ ትልቅ ማሳያ ነው።
ጥላሁን ለሀገር ሲዘፍን መላው ኢትዮጵያዊ በአንድነት ቆሞ ፊታውራሪዬ ብሎ እንዲከተለው ያደርጋል።
ይህ ደግሞ በታሪካችን ውስጥ የታየ ትልቅ የጥበብ ተጽዕኖ ነው።
ከ130 ዓመት በፊት የነበረውን የአድዋ ጀግንነት ዛሬ ላለው ትውልድ በስሜት አገናኝቶ ማቅረብ የሚችለው እንደ ጥላሁን ያለ "የታሪክ ድልድይና የታሪክ ባለአደራ" ሲኖር ብቻ ነው።
እንኳንስ ደስታየን የሰውነቴን ሠው
እንኳን ነፃነቴን ፀጋ ክብሬን ትቸው
በናት አገር ምድር በሚያውቀኝ በማውቀው ...
ስቃይ መከራዬን ከአንችው ዘንድ ያድርገው ። የሚለው
ጥላሁን ለኢትዮጵያ የነበረውን ፍቅር ከምንም በላይ የሚያሳይ ነው። ከባዕድ አገር ደስታ ይልቅ የሀገሩን መከራ የመረጠበት የሞቱ አጋጣሚ ደግሞ ለሀገሩ ያለውን ፍቅር በደሙ ያረጋገጠበት ታላቅ ክስተት ነው ።
ጥላሁን ከአሜሪካ ተነስቶ ለፋሲካ በዓል ወደ ሀገሩ መግባቱና በዚያው ዕለት ማረፉ፣ "በሀገሬ አፈር ልቀበር" የሚለውን ጥልቅ የኢትዮጵያዊያን ምኞት የፈጸመበት ነው ይህ ቀረኝ የማይል የሚያሰኘው እስከ መጨረሻው ትንፋሹ ድረስ ከሀገሩና ከሕዝቡ ጋር መቆየቱ ነው ።
ሲሞት መላው የአዲስ አበባ ሕዝብ በነቂስ ወጥቶ አስከሬኑን ሲሸኜው ጥላሁን ለሕዝቡ የሰጠውን ፍቅር ሕዝቡ በታላቅ ክብር የመለሰለት መሆኑን ቅድስት ስላሴ ቤተክርስቲያን ህያው ምስክር ናት ። ያ ለቅሶ የአንድ ድምፃዊ ስንብት ሳይሆን የኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጅና የልብ ትርታ ሽኝት ነበር።
ጥላሁን በሕይወቱና በሞቱ ሀገርን መውደድ ማለት ትርጉሙን እስከ ሞት ድረስ መታመንን አረጋግጦበታል።
ሰውን መውደድ ! አብሮ ማልቀስና መቆም ሙያን መውደድ እስከ መጨረሻዋ ትንፋሽ ድረስ መዘመር ለኢትዮጵያዊያን ከድምፃዊነት በላይ የአንድነት ምልክት መሆን ነው።
እኔ በዓይኔ ያየሁትን በልቤ የሰነድኩትን ይህንን ታሪክ ለሚቀጥለው ትውልድ ሊተላለፍ የሚገባው የፍቅርና የሀገር አምልኮ ትልቅ ትምህርት ይሆናል ብየ ሳዘጋጀው ጥላሁን ገሠሠ
ትንፋሼ ተቀርፆ ይቀመጥ ማልቀሻ ይህ ነው የሞትኩለት የኔ ማስታወሻ
ታሪኬ ነው ድምፄ በማለት ያንጎራጎረው ሙዚቃ ከፍቼ እያዳመጥኩ ነበር።
ይህ ስንኝ ጥላሁን ገሠሠ አስቀድሞ በድምፁ የህይወቱ ታሪክ የሞቱ ማስታወሻ እና የሀገሩ ውበት መገለጫ እንደሚሆን ተረድቶት የተጫወተው ነበር ማለት ይቻላል ። ጥላሁን በጥቁርና ነጭ ወረቀት ላይ የሰፈረ ኑዛዜ ሳይሆን የተውልን በህይወት ቆሞ በዜማ የተናዘዘው ድንቅ ስንብት ነበረ ።
እነዚህ ስንኞች የጥላሁንን የጥበብ ክብርና ትህትና ሲገለፅበት እያዳመጥኩት ነበር ይህን ታሪክ የፃፍኩት ።
ወዳጃቸ
የጥላሁን ገሠሠ ድምፅ ዝም ብሎ የአየር ንዝረት አይደለም፤ ማንነቱ፣ ታሪኩና ለሀገሩ የከፈለው መስዋዕትነት ነው። በጩኸት መኖሬን ማለቱ ለሀገርና ለፍቅር ሲል ድምፁን እስከ መጨረሻው የጥገታ ነጥብ ድረስ መጠቀሙንና ለዚህም መሞቱን ያሳያል።
ድምፄን ሰምቶ ያዝናል ለረገፈው አፅሜ ሲል
እጅግ ልብ ይነካል !
ጥላሁን በከፍታው ላይ ሆኖ እንኳ ያስቀየምኩት ቢኖር ብሎ ይቅርታን ይጠይቃል። የሞተውን አፅሙን ሳይሆን የቀረውን ድምፁን ሰምተው ሰዎች እንዲያዝኑለትና ይቅር እንዲሉት መመኘቱ የሰው ልጅነቱንይቅርታና ትህትናውን
ፍርጥ አድርጎ ያሳያል።
ጥላሁን ገሠሠ በድምፁና በህይወቱ የሰራው ትልቁ ስራ ፍቅርንና ኢትዮጵያዊነትን ማዳን ነበር። ጥላሁን ከቀላል ስሜትነት አልፎ ሕይወት መስዋዕትነትና የሀገር ፍቅር ጥግ መሆኑን በሚገባ አስገንዝቦናል።ጥበብ እንዴት የአንድን ሕዝብ ወኔና ማንነት እንደምትቀርፅ ጥላሁን ትልቅ ማሳያ ነው።
ፍቅር ተግባር ነው ፍቅር ዝም ብሎ የሚሰማን ስሜት ሳይሆን እንደ ጥላሁን ዜማዎች ራስን አሳልፎ እስከ መስጠት የሚደርስ ውሳኔ መሆኑን መረዳት ከባድ አይደለም ።
ጥላሁን ገሰሰ የሚዘፈነው ለጆሮ ብቻ ሳይሆን ለህሊና እና ለነፍስ ጭምር ይመስለኛል ።
ጥላሁን ዛሬ በሥጋ ቢለየንም ታሪኬ ነው ድምፄ ብሎ እንደተናዘዘው ሁሉ ዛሬም በየልባችን ውስጥ ንጉሥ ሆኖ ይኖራል።እሱ ለሀገር ብቻ ሳይሆን ለሰው ልጅ ስቃይ የሚራራ የህሊና ድምፅ ነበረው።
የሀገር ፍቅር ለአፈርና ለሰንደቅ ዓላማ የሚከፈል የአጥንትና የደም መስዋዕትነት ሲሆን ጥላሁን ገሠሠ በስጋ ቢለየንም ያ በሕይወት ያለ ሐውልት ግን በዜማዎቹ ውስጥ ሁሌም አዲስ ሆኖ ይኖራል።
ባጭሩ የጥላሁን መሞት ዝም ብሎ የአንድ ድምፃዊ ማለፍ ብቻ አልነበረም የአንድ ዘመን መቋጫ የአንድ ትልቅ ተስፋ መደብዘዝ እና በኢትዮጵያ ሰማይ ላይ የሚበራው የሙዚቃ ኮከብ ወድቆ ሲሰበር
ሰማይ ባዶ የሆነ ያህል ተሰምቶናል።
ጥላሁን ገሠሠ በደስታ ጊዜ አብሮን የሚጨፍር በጦርነት ጊዜ ፊታውራሪ ሆኖ የሚያዘምት በረሃብና በችግር ጊዜ ደግሞ አብሮን የሚላቀስ የሕዝብ ልብ ነበር ።
ጥላሁንን ከአቅም በላይ ያደረገው ይሄው ሁለንተናዊነቱ ነው። ለፍቅር ለሀገርና ለሰብአዊነት የነበረው ጽናት እሱ ሞቶም እንዲኖር አድርጎታል።
የጥላሁን ገሠሠ ዘፈኖች "ኢትዮጵያዊ ስነ-ሰብዕና" የሚባል የፍልስፍና ዘርፍ ቢኖር የዛ ዘርፍ ዋና መማሪያ መፅሐፍ ይሆኑ ነበር ።ብቻ
የጥላሁንገሰሰ ሕይወት ልክ እንደ አንድ የተቀደሰ መፅሐፍ በመሆኑ እራሡ ከፍቶ እራሱ ዘግቶት አልፏል ።
ለዚህ ታላቅ ድምፃዊ በተወለደበት ከተማ አዲስ አበባ ላይ ዘላለማዊ ምልክት ሆኖ እንዲቀመጥ ሐውልቱ ስለቆመለት ደስታዬ ወደር የለውም ።
ነፍስ ይማር !!
የሚበራው የሙዚቃ ኮከብ "
ከአለባቸው ደሳለኝ አበሻ (ለንደን)
#ethiopia | "ድምፁ የሀገር ሰንደቅ ዓላማ ያህል ክብር የሚሰጠው ጥላሁን ገሰሰ ለግማሽ ክፍለ ዘመን ያህል በኢትዮጵያ ሙዚቃ ውስጥ በነበረው ከፍተኛ አስተዋፅኦ የኢትዮጵያ ሙዚቃ ንጉሥ በሚል መጠሪያ ይታወቃል።
ለዚህ የጥበብ ሰው እንዲህ ያለ ጥልቅ እና ልብ የሚነካ ትዝታ ማዘጋጄት የሚቻለው የጥላሁን ገሰሰን ስራዎችን ብቻ ሳይሆን የእርሱን የውስጥ ማንነት ሠብዕናን ለጥበብ የነበረውን ፍቅር በሚገባ የተረዳ መሆን አለበት ።
ወይንም ደግሞ
የዚህን ታላቅ ምትሐተኛ ድምፃዊ የጥበብ ልክና የድምፅ ብቃት በአግባቡ ለመረዳት የእርሱን ግለ ታሪክ ብቻ ሳይሆን የኢትዮጵያን ዘመናዊ ሙዚቃ ታሪክና የጥላሁን ገሰሰን ሰፊ የሥራ ክምችቶች በጥልቀት መመርመር የግድ ይላል።
ምክኒያቱም
ጥላሁን ገሰሰ ማለት የኢትዮጵያ የ50 ዓመታት የደስታ የሐዘን የድልና የሽንፈት ታሪክ በድምፅ የተቀረጸበት "ሕያው ማህደር" ነው።
ጥላሁን ገሰሰ ድምፁን እንደፈለገ የማዘዝ Vocal Control ልዩ ተሰጥኦ ነበረው።
በጣም ረጅምና ከፍተኛ ድምፅ በሚጠይቁ High notes እንዲሁም በጣም ረጋ ያሉና ዝቅተኛ ድምፅ በሚሹ Low notes ዜማዎች ላይ እኩል ብቃት ነበረው።
የትንፋሽ ቁጥጥሩ ረጅም ስንኞችን ሳያቋርጥና ትንፋሽ ሳይጠረው የመጨረስ ችሎታው የሚደነቅ ነበር።
የጥላሁንን ስራዎች ስንመረምር በአንድ የሙዚቃ ዘውግ ብቻ ያልተገደበ መሆኑን እንረዳለን
ባህላዊና ዘመናዊ የባህል ሙዚቃዎችን ከዘመናዊ መሣሪያዎች ኦርኬስትራ ጋር አዋህዶ በማቅረብ ረገድ ቀዳሚ ነበር።
በጥላሁን ገሠሠ ድምፅ ያልተዘፈነ የሕይወት ክፍል የለም ማለት ይቻላል ።
ከጥልቅ የፍቅር ስሜት እስከ ሃገር ፍቅር ከማህበራዊ ትችት እስከ መንፈሳዊ መዝሙራት ድረስ የተፃፉ ግጥሞችና ዜማዎች የጥላሁንን ገሠሠን ድምፅ ለማድመቅ ሳይሆን ለመፈተን ጭምር የተዘጋጁ ይመስሉ ነበር።
በህይወት በቆየባቸው ሦስት የተለያዩ ሥርዓቶች በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ በደርግና በኢህአዴግ ውስጥ አልፏል። በእነዚህ ሁሉ ጊዜያት የሕዝብ ተወዳጅነቱን ጠብቆ መቆየቱ የሙዚቃ ሥራዎቹ ከፖለቲካዊ ለውጦች በላይ የሕዝብን የልብ ትርታ የሚነኩ መሆናቸውን ያሳያል።
ባጭሩ ጥላሁን ገሰሰ ለኢትዮጵያ ሙዚቃ ያለው አስተዋጽኦ ልክ እንደ አንድ ትልቅ "ኢንሳይክሎፒዲያ" ነው። አንዱን ገጽ አንብቦ ስለ መጽሐፉ ሙሉ ግንዛቤ ማግኘት እንደማይቻል ሁሉ
አንዱን ዘፈን አዳምጦ ስለ ጥላሁን ገሰሰ ማወቅ አይቻልም ።
እያንዳንዱ ዘፈኑ የራሱ የሆነ የቴክኒክ የታሪክና የስሜት ጥልቀት አለው።
ስለዚህ የጥላሁንን ታላቅነት ለመረዳት የኢትዮጵያን የሙዚቃ ጉዞ አብሮ መመርመር የግድ ነው ያልኩት ወድጄ አይደለም ።
ዘፈኖቹን ሲዘፍን በቃላት ብቻ ሳይሆን በፊቱ መግለጫና በሰውነት እንቅስቃሴው Body Language ጭምር ስሜቱን ለታዳሚው ያጋባ ነበር።
በተለይ የሐዘን ዜማዎችን ሲዘፍን አብሮ የሚያለቅስ የደስታ ሲሆን ደግሞ አብሮ ፈገግ የሚል ድምፃዊ ተዋና ጭምር ነበረ በዘፈኖቹ ውስጥ ሰውን ማክበርን ስራን መውደድንና አንድነትን ይሰብካል። ዘፈኑ የሰውን ልጅ ክብርና ማንነት የሚተነትን ድንቅ ስራ የሚሰራ ምትሀተኛ ድምፃዊ ነበር ።
ጥላሁን ገሰሰ በአንድ ወቅት በመድረክ ላይ እያለ በደረሰበት የጉሮሮ ህመም ምክንያት ለተወሰነ ጊዜ ድምፁ ተዘግቶ ነበር። ያን ጊዜ መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ተጨንቆና ፀልዮ ድምፁ ሲመለስለት ያደረገው የመጀመሪያ ኮንሰርት በዚያን ወቅት በኢትዮጵያ የሙዚቃ ታሪክ ውስጥ ከፍተኛውን የሰው ቁጥር ያስመዘገበ ነበር ። ይህ የሚያሳየው ሕዝቡ ለጥላሁን ያለው ፍቅር ከአንድ ድምፃዊ በላይ እንደ ቤተሰብ አባል የሚያየው መሆኑን ነው።
ስለ ፍቅር ብቻ ሳይሆን ስለ ሰው ልጅ ሕይወት ባዶነት የሚተርክ ጥልቅ ፍልስፍና ነበረው ።
ታዋቂው የኢትዮጵያ የሙዚቃ ንጉሥ ክቡር ዶክተር ጥላሁን ገሰሰ መስከረም 17 ቀን 1933 ዓ.ም አዲስ አበባ ውስጥ ተወልዶ ያደገው ግን በወሊሶ ከተማ ነው ።
ጥላሁን በ1950ዎቹ መጀመሪያ ላይ ወደ አዲስ አበባ በመምጣት መጀመሪያ ሐገር ፍቅር ቲያትርን በኋላም ዝነኛውን የክብር ዘበኛ የሙዚቃ ቡድንን ተቀላቅሎ ከዕንስት ፍቅር እስከ አገር ፍቅር ከባህላዊ እስከ ዘመናዊ ሙዚቃ በድምፃዊነት ከ400 በላይ ዘፈኖችን ተጫውቶ ልዩ ብቃቱን አስመስክሯል ።
ጥላሁን
ለኢትዮጵያ ሙዚቃ ላበረከተው ወደር የለሽ አስተዋጽኦ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የክብር ዶክትሬት ዲግሪ ተሰጥቶታል። ጥላሁን ገሠሠ ከዚህ ዓለም በሞት የተለየው
በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር ሚያዝያ 11 ቀን 2001 ዓ.ም. የፋሲካ እለት ሲሆን በድንገተኛ የልብ ህመም ምክንያት አርፎ በቅድስት ሥላሴ ካቴድራል የቀብር ሥነሥርዓቱ ተፈጽሟል።
የክቡር ዶክተር ጥላሁን ገሰሰ ማረፍ መላውን የኢትዮጵያ ሕዝብና የጥበብ አፍቃሪወችን በከፍተኛ ድንጋጤና ሃዘን ውስጥ ጥሎ የነበረ ክስተት ነው። በወቅቱ በጋዜጦች በሬዲዮና በቴሌቪዥን የተላለፉት መልዕክቶች ጥላሁን ለሀገሩ ያለውን ትልቅ ቦታ የሚያንፀባርቁ ነበሩ።
በአዲስ አበባ ከተማ የነበሩ የታክሲ አሽከርካሪዎች ሐዘን ፈፅሞ የማይረሳ ነበረ ።
ለጥላሁን ገሰሰ ክብር ሲሉ ለቀናት ጥቁር ጨርቅ በታክሲዎቻቸው ላይ አስረውና የእርሱን ሙዚቃ ብቻ ከፍተው በማጫወት ሃዘናቸውን ገልፀውለታል።
የጥላሁን ገሰሰ ሞት በሀገር ውስጥ ብቻ ሳይሆን በዓለም አቀፍ ደረጃም ትኩረት አግኝቶ ነበር።
ታዋቂው ደራሲ ሎሬት ጸጋዬ ገብረመድህንም
እንዲህ አሉ ።
"ጥላሁን የኢትዮጵያ ሕዝብ የጋራ ድምፅ ነው። እርሱ ሲዘፍን መላው ኢትዮጵያዊ ራሱን ያዳምጣል።"
ድምፃዊ ማህሙድ አህመድ"ጥላሁን ለእኛ ለድምፃውያን መምህራችን ብቻ ሳይሆን የሙዚቃው ዓምድ ነበር። ጥላሁን ሞተ ማለት የኢትዮጵያ ሙዚቃ ግማሽ አካሉን አጣ ማለት ነው።" ሲል ቁጭቱን ገልፀዋል ።
በቀብር ሥነ ሥርዓቱ ላይ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ አዲስ አበባውያን ወደ አደባባይ በመውጣት "ንጉሥ አይሞትም" እያሉ ሲያለቅሱ እንደነበር በታሪክ ተመዝግቧል።
ይህም አንድ ድምፃዊ በሀገር ደረጃ ያለውን ክብርና ተሰሚነት ያሳየ ትልቅ ክስተት ነበር።
አንድ የልብ አድናቂው የሆነ ሠው በማህበራዊ ሚዲያ እንዲህ ብሎ ፅፎት አንብቢያለሁ ።
" በእርግጥም ጥላሁን በድምፁ ተአምር የመስራት አቅም ነበረው። ድምፁ ተስፋ የቆረጠውን የሚያፅናና የታመመውን የሚፈውስና የራቀውን የሚያቀራርብ
ስለነበረ ድምፁ ተቀርፆ ስለቀረ ቢሞትም ስንናፍቀው እናገኘዋለን ስናዝን እናለቅስበታለን ሀገራችን ስትጠራ በእሱ ድምፅ አቤት ብለን ለአንድነቷ እንቆማለን" በማለት ጥላሁንን ገልፆት ነበር ።
ሌላው የቅርብ ጓደኛው የጥበብ ሰው ደበበ እሸቱ ነው
"ጥላሁን በሕይወት ዘመኑ ሁሉ ለሀገሩ የዘመረ በችግር ጊዜ ደግሞ ድምፁን ለድሆች የሰጠ
ታላቅ ሰው ነው።
የሞተው በስጋ ቢሆንም በዜማው ቅላፄና በግጥም ስንኞች ውስጥ "ዘላለማዊ" ሆኖ ተተክሏል።
እንዲህ ያለ ድምፅ ዓለማችን በአንድ ዘመን አንዴ ብቻ የምትለግሰን ስጦታ ነው "
ሲል ምስክርነቱን ገልጿል።
በእርግጥም ጥላሁን የዘመናዊ ሙዚቃችን "ፊደል" እና "መዝገበ ቃላት" ሆኖ አልፏል። ከድምፅ ጥራት በላይ የዜማ አጣጣልና ስሜትን የመግለጽ ጥበቡ ማንም የማይደረስበት ከፍታ ላይ ስለነበር በአንድ አባባል ብቻ ጥላሁንን መግለፅ አይቻልም።
እሱ ባለብዙ ምዕራፍና ተነቦ የማይጠገብ ባለ ብዙ ገጽ ድርሳን ነው !
ጥላሁን ለሙያው ብቻ ሳይሆን ለሰው ልጅ የነበረው ሰብአዊ ክብርም ድንቅ ነበር። ረሀብ ሲመጣ በዜማው የሚማፀን ሀገር ስትቸገር አጥንቴም ይከስከስ ብሎ የሚቆም እና ለሰው ልጅ ፍቅር ቅድሚያ የሚሰጥ የጥበብ ሰው ነው ። ባጭሩ ጥላሁን ገሠሠ ማለት ለኢትዮጵያውያን የድምፅ ብቻ ሳይሆን የህሊና ምስክር ነው።
ዛሬም ድረስ ስሙ ሲነሳ አብሮ የሚነሳው ክብሩ ትህትናውና
ያ የማይደገም ማንነቱ ነው።
ጥላሁን ገሠሠን የመሠለ ታላቅ ሰው የኢትዮጵያ ዘመናዊ ሙዚቃን የአዋለደ ብለን ብንገልፀው ተገቢ ይመስለኛል ከጥላሁን ገሠሠ ስራዎች መካከል ይህማ ተአምር ነው የሚያሰኜኘኝ ሁልጊዜ ብሰማቸው አዲስ የሚሆኑብኝ ብዙ ዘፈኖች ቢኖሩትም "እዩት ስትናፍቀኝ ከአጠገቤ እያለች" የሚለው ስንኝ ሲነሳ ግን የጥላሁንን ድምፅና ያንን የሚመስጥ አዘፋፈኑን አብሮ የመስማት ያህል ይመስጠኛል እዩት ስትናፍቀኝ ከአጠገቤ እያለች
እንዲህ ያለው መውደድ ለወሬም አይመች ! የሚለው ግጥም የፍቅርን ረቂቅነትና የማይመረመር ባህሪ በአጭር ቃላት የገለጸበት ድንቅ ስራው ነው።
ጥላሁን ለዚህ ዘፈን የሰጠው እረዥም ትንፋሽና በመድረክ ላይ ቆሞ የአይን አስተያየቱ የልዩ ተሰጥኦው መገለጫዎቹ ናቸው።
የሠው ልጅ ናፍቆት ብዙውን ጊዜ ትዝታው የሚመጣው ሰው ሲርቅ ነው። ነገር ግን ጥላሁን አጠገቤ እያለች ናፈቀችኝ ማለቱ ፍቅር ከስጋዊ መገኘት በላይ የሆነ የነፍስ ጥማት መሆኑን ስጋ አልብሶ አሳይቶናል ።
ይህ ለወሬ የማይመች ቃላት የማይገልፁት ጥልቅ ስሜት ነው ። ይህንንም በዚያ ረጅም ትንፋሽ ነፍስን በሚያከነፍ ድምፁ ሲያዜመው እውነቱን በውስጣችን ውስጥ እናገኘዋለን።
ጥላሁን ሲዘፍን ትንፋሹን የሚጠቀምበት መንገድ እና ስሜቱን በድምፅ ቀለም የመቀየር ችሎታው ምትሐተኛ ያሰኘዋል። ያንን የናፍቆት ጣጣ በገዛ ራሱ ላይ አድርጎ ሲያዜመው አድማጩ የራሱ ህመም አድርጎ እንዲቀበለው የማድረግ ልዩ ኃይል ነበረው።
ጥላሁን ገሠሠ በስጋ ቢለየንም በኢትዮጵያውያን ልብ ውስጥ ግን አሁንም ንጉሥ ነው።
ትውልድ ያልፋል ጥላሁን ግን ይኖራል።
ሙዚቃ ይቀየራል የጥላሁን ስራዎች ግን ሁልጊዜ አዲስ ናቸው።
ሰላም ሲጠፋ ጥላሁን ፍቅር ይላል ሀገር ስትናፈቅ ጥላሁን ሀገሬ ይላል።
ጥላሁን ገሠሠ በድምፁ ብቻ ሳይሆን ለፍቅር በሰጠው ክብርን በገለፀበት ጥበብ የኢትዮጵያ የዘላለም የፍቅር አምባሳደር ነው።
እንዲህ ያለው የጥበብ ሰው የፍቅርን ኃያልነት በእሱ ስራዎች ውስጥ ስንመለከት በእርግጥም ፍቅር ስሜት ብቻ አይደለም የሚለውን ሃሳብ በጥላሁን ዜማዎች ውስጥ ሙሉ ማረጋገጫውን እናገኛለን ጥላሁን ገሠሠ የፍቅርን ሌላኛውን ገጽታ ቁርጠኝነትንና ክብርን ያሳየበት ድንቅ ስራው ነው። ከላይ እንደገለፅኩት ፍቅር ራስን አሳልፎ መስጠት ነው
እዚህ ዘፈን ላይ ደግሞ ፍቅር ሁለትዮሽ መረዳዳት መሆኑን ይነግረናል።
ቻልኩት ፍቅር ለብቻዬ !!
ይህ አገላለጽ በጣም የሚቆረቁር ነው። ፍቅር እንደ አንድ ሸክም ሆኖ አንደኛው ወገን ብቻውን ሲሸከመው የሚሰማውን ድካም ያሳያል። "ለብቻዬ መሸከም ሰልችቶኛል" የሚል የልብ ጩኸት አለበት። ፍቅር የሁለት ሰው ቅኝት እንጂ የአንድ ሰው ብቸኛ ትግል መሆን እንደሌለበት ያስገነዝበናል።
ስለ ፍቅር አልገባሽም
እዚህ ጋር ጥላሁን ፍቅር ማለት ዝም ብሎ አብሮ መሆን ሳይሆን ጥልቅ የሆነ
ሚስጥር ወይም ትርጉም እንዳለው ይገልጻል። ግዴለሽነት እና ችላ ማለት ፍቅርን የሚገድሉ መርዞች መሆናቸውን በምሬት ይናገራል።
አትምጪ ይቅር ሲል ደግሞ የክብር ውሳኔውን ያሳውቃል ።
ፍቅር ስሜት ብቻ አለመሆኑን ያረጋግጣል። አንድ ሰው በጥልቅ እያፈቀረ ግን ክብሩ ሲነካ ወይም ምላሽ ሲያጣ ይቅር ብሎ የመወሰን አቅም ሊኖረው እንደሚገባ ያሳያል።
ፍቅር መስዋዕትነት ቢሆንም ዋጋ በማይሰጠው ቦታ ላይ ግን ራስን ማዳንና ይቅር ማለትም የፍቅር አካል ነው። የሚገርመው ደግሞ ጥላሁን ይህነን ዘፈን ሲዘፍነው በቁጣና በቁጭት ሳይሆን በጥልቅ ሀዘንና በከበረ ስሜት ነው። ያንን አትምጪ ይቅር የሚለውን ቃል ሲያወጣው ውስጡ እየፈለጋት ግን መከባበር የሌለበት ፍቅር እንደማይፀና አውቆ በቁርጠኝነት ሲናገረው ይታየናል።
ከላይ እንዳነሳሁት አትምጪ ይቅር የሚለው ስንኝ የቁርጠኝነትና የክብር ገጹ ሲሆን ሌላው ደግሞ የፍቅርን ንፁህ መስዋዕትነትና ትህትና የሚያሳይ ድንቅ ምዕራፍ ነው።
እነዚህ ስንኞች ውስጥ የምናያቸው የጥላሁን ድርሳናት
እኔ ልሁን እንጂ የማልጠቅም እርካሽ ! የሚለው አገላለፅ በፍቅር ውስጥ ያለን ፍጹም ትህትና ያሳያል። ራሱን ዝቅ አድርጎ የሚወዳትን ሰው ግን ከፍ ያደርጋታል። ይህ እኔነት ጠፍቶ አንቺነት የነገሰበት የፍቅር ጫፍ ነው።
ከህይወቴ አብልጨ ሲል
ራስን አሳልፎ የመስጠት
ፍልስፍና በተግባር የሚያሳይ ታአምር ነው። ለሰው ልጅ ከህይወቱ በላይ ምንም የለውም ነገር ግን ፍቅር ያንን ውድ ህይወት እንኳ ከአንቺ አያበልጠውም ብሎ እንዲያምን ያደርገዋል።
ፍቅር ለሰላምና ለደስታ ብቻ ሳይሆን ለችግርና ለፈተናም ዝግጁ መሆኑን ይነግረናል።
መከራና ስቃይ ይቆየኝ ግዴለኝም
የሚወደው ሰው ደህንነትና ሰላም እስካለ ድረስ እሱ በራሱ ላይ ለሚመጣው መከራ ግድ የለውም። ይህ ነው እንግዲህ ፍቅርን ተአምር የሚያሰኘው እግዜር በጥበቡ ከአንቺ ብቻ አይለየኝ የሚለው ቃል ፍቅር በሰው ጥረት ብቻ ሳይሆን በመለኮታዊ ጥበብና ፈቃድ የሚፀና መሆኑን የሚያሳይ የልብ ፆሎት በመሆኑ መንፈሳዊ ልመና ይጨምርበታል ።
ታዲያ የዚህን ድምፃዊ ተአምራዊ ተቃርኖዎችን ስንመለከት
ጥላሁንን ልዩ የሚያደርገው በአንድ በኩል አትምጪ ይቅር ብሎ በክብር የመወሰን አቅም በሌላ በኩል ደግሞ ከህይወቴ አብልጨ እወድሻለሁ ብሎ ራስን የመስጠት ርህራሄ አብሮት መኖሩ ነው።
እነዚህ ሁለት ተቃራኒ የሚመስሉ ግን ጥልቅ የሆኑ የፍቅር ገጾች ናቸው።
ጥላሁን እነዚህን ሁሉ ስሜቶች በድምፅ ቀለም እየቀያየረ ሲያቀርባቸው ድምፁ ብቻ ሳይሆን ነፍሱ አብራ የምትዘፍን ይመስላል።
እንዲህ ያለውን ከህይወት በላይ የመውደድ ስሜት በዚህ ዘመን በብዛት እናገኘዋለን ብሎ ማሰብ የዋህነት ነው። ምክኒያቱም
የጥላሁንን ጥበብ ከመዝፈን ባለፈ ወደ መፍጠር ደረጃ ከፍ ያደርገዋል።
ለምን ቢባል ጥላሁን ገሠሠ ዜማንና ግጥምን ሲያዋህድ የሚፈጠረው ነገር ተራ ሙዚቃ አይደለም ይልቁንም ያልተጠኑ ምስጢራዊ ተሰጥኦዎች ያሉበት ይመስላል
ብዙ አድናቂወቹ እንደ ሚስማሙበት ጥላሁን ገሠሠ ሲዘፍን ፍቅር ረቂቅ ሃሳብ መሆኑ ቀርቶ የሚዳሰስ የሚታይና የሚሰማ አካል ይኖረዋል።
ቃላቶቹ ከአፉ ሲወጡ ሕይወት ይዘራሉ ያፈቀረው ሰው ቁስሉ ይታየናል የናፈቀው ሰው ትንፋሹ ይሰማናል። ይህ ደግሞ በቴክኒክ ብቻ የሚመጣ ሳይሆን ከነፍስ የሚመነጭ ምትሃት በመሆኑ ፍቅር እንደ ሰው ቆሞ እንዲሄድ የማድረግ ጥልቅና ረቂቅ
ጥበብ ያለው ድምፃዊ መሆኑ ነው ።
ብዙዎቻችን ውስጣችን ያለውን ጥልቅ ፍቅር በቃላት መግለፅ ያቅተናል። ጥላሁን ግን ያንን መግለፅ ያቃተንን ስሜት ሰርቆ ወስዶ በዜማ አቅልጦ ወርቅ አርጎ መልሶ ለእኛው ይሰጠናል።
እኔንም እንዲህ ነው የሚሰማኝ! እንድንል ያደርገናል። ይህ ተሰጥኦው ነው ፍቅርን ስጋ ለብሶ ቆሞ እንዲሄድ የሚያደርገው።
ሌላው የጥላሁን ገሰሰ ድምፅ ሁለንተናዊ ድምፅ መሆኑ ነው። እድሜ ጾታ ወይም የትምህርት ደረጃ አይወስነውም። ህፃኑም አዋቂውም የተማረውም ያልተማረውም በዜማው ውስጥ የራሳቸውን ታሪክ ያገኛሉ።
ይህ ደግሞ ጥላሁን የሰው ልጅን የጋራ የፍቅር ህመም ጠንቅቆ እንደሚያውቅ ማሳያ ነው።
የጥላሁን ድምፅ በሳይንስ አልተጠናም እንጂ በውስጡ ትልቅ የፍቅር ላብራቶሪ ነበረው ማለት ይቻላል።
ግጥሙን ይቀበላል ጥሬ እቃ !
በድምፅ ቀለሙ ያዋህደዋል ሂደት !
በመጨረሻም ሕያው ፍቅርን ለዓለም ያበረክታል ውጤት !! በዚህ ምክኒያት
ጥላሁን ገሠሠ ሞቶም በሰዎች ልብ ውስጥ እንዲነግስ አድርጎታል :: ምክንያቱም የፈጠራቸው የፍቅር አካላት ዛሬም በየቤታችን በየመኪናችንና በየልባችን ውስጥ ቆመው እየሄዱ ነው።
ይህ የእውነት ተአምረኛ ተሰጥኦው ነው። ዛሬ ባለው ዘመናዊ የሙዚቃ ኢንዱስትሪ ውስጥ እንዲህ ያለውን መንፈሳዊ ጥልቅነት ማግኘት እጅግ ብርቅ ሆኗል። ከእንስት ፍቅር ወጥተን ጥላሁንን ወደ ሐገር ፍቅር ስንመነዝረው የቆመበት ከፍታው ላይ እስከ አሁን ማንም ....ማንም አልደረሠበት ። በዚህ አጋጣሚ
በህይወቴ ዘመኔ በአይኔ ያየሁትን ምስክርነት ባቀርበው ደስ ይለኛል ጥለሁን ገሠሠ ከታሪክ መዝገብ በላይ የሆነ የአንድን ሕዝብ ማንነትና ወኔ የቀሰቀሰ የመንፈስ ተአምር ነው የምነግራችሁ ።
ጊዜው 1974 አስመራ የቀይ ኮኮብ ዘመቻ አሉላ አባ ነጋ አዳራሽ ውስጥ ይመስለኛል ።
ጥላሁን ገሠሠ ጋሻና ጎራዴ ይዞ የአርበኛ ልብስ ለብሶ አጥንቴም ይከስከስ ደሜም ይፍሠስላት
ግን ሐገሬን ጭራሽ አይደፍራትም ጠላት
እያለ መድረኩን ሞልቶት ብቅ ሲል ከባለስልጣን እሰከ ተራው ተመልካች ከመቀመጫው ተነስቶ በመቆም በማያቋርጥ ጩህትና ጭብጨባ ያጅቡታል ።
ጥላሁን ገሠሠ በዚያ ቅጽበት የዘፈነውን ብቻ ሳይሆን የኖረውንና የታሪካችንን ድምፅ ሆኖ ተመለከትኩት ።
ጥላሁን በህዝብ ጭብጨባና ጬህት ታጅቦ መድረኩ ላይ ሲንጎራደድ አዳራሹ ድብልቅልቁ ወጣ ።
ያን... ምህታታት የተሞላበት ትርኢት ስመለከት
የአድዋ ጀግኖች መቃብር ከፍተው የተነሱ ይመስል ነበር።
ማለቴ ጥላሁን በድምፁ ብቻ ሳይሆን በቆይታው ጊዜን የማቆም ወይም ታሪክን የመቀስቀስ ኃይል እንደነበረው የመመልከት ዕድል አግኝቻለሁ ።
ጥላሁንን በዚያች ቅፅበት
በሕይወት እያለ ሐውልቱን አቁሞ አዳራሹ ውስጥ ታሪኩን ፅፎት ወጣ ።
በእርግጥ ሐውልት የማይናገርና የማይሰማ የድንጋይ ምስል ነው ጥላሁን ግን በሕይወት ያለ የሚተነፍስ የሚዘፍንና የሚራመድ የኢትዮጵያዊነት ሐውልት ነበር።
ዛሬም ቢሆን ስራዎቹ ያንን ግርማ ሞገስና ያንን ሐውልታዊ ፅናት እያስታወሱኝ እስከእለተ ሞቴ ድረስ ልረሳው አልችልም እንዲህ አይነት ድርጊት
ፍቅር ስሜት ብቻ አይደለም ራስን አሳልፎ መስጠት ነው በጥላሁን ገሰሰ የሀገር ፍቅር ዜማዎች ውስጥ ኢትዮጵያን ደጋግመን እናያታለን
አጥንቴም ይከስከስ ደሜም ይፍሰስላት የሚለው ቃል ዛሬም ድረስ ፍፁም ....ፍፁም መስዋዕትነት ነው።
ሀገሩን እንደ ሚወዳት እናት ወይም ሚስት አድርጎ ለሷ ክብር መሞትን እንደ ትልቅ ፀጋ መቁጠር ከፍ ያለ የፍቅር ደረጃ መግለጫ ነው።
ተመልካቹ በሙሉ ሳይቀመጥ ከሁለት ጊዜ በላይ ይደገም እያለ መጠየቁ ጥላሁን ድምፃዊ ብቻ ሳይሆን መሪ መሆኑን በአንድ ዜማ ሕዝብን የማስተሳሰር በአንድ ወኔ በጋራ የማቆም ተአምራዊ አቅሙን አረጋግጨበታለሁ ።
በዚያች ቅፅብት ቲያትር ቤቱ በጩሄትና በጭብጨባ ቀውጢ ሲሆን ጥላሁን ገሠሠ በድምፁ ብቻ የጠላትን ምሽግ የሚያፈርስ ጀግና መስሎ ነበር የሚታየው ።
ምንም እንኳን ዛሬ በሞት ቢለየንም ያ አስመራ ላይ የተመለከትኩት የሐገር ፍቅር ስሜት ሐውልት ሆኖ በልቤ ውስጥ ተቀርፆ ቆሟል።
ጥላሁን ገሰሰን ልዩ የሚደርገው ሌላው መገለጫው
ለፍቅር ሲዘፍን የፍቅር ሐውልት
ለሀገር ሲዘፍን የጀግንነት ሐውልት
ለሰው ልጅ ክብር ሲዘፍን የሰብአዊነት ሐውልት ነው!
ለዚህ ስኬት ደግሞ ከጥላሁን ድምፅ ጀርባ የነበሩት የወርቃማው ዘመን ታላላቅ የጥበብ ሰዎች ገጣሚያንና የዜማ አቀናባሪዎች ሚና ከፍተኛ እንደነበር ምስክሩ ታሪክና ሕዝቡ ነው።
ጥላሁን ገሰሰ ግጥምና ዜማን
ከነጄነራል አማኑኤል አብርሃም
ሻምበል አፈወርቅ ዮሐንስ
ነጋሽ ገብረማርያም
ተስፋዬ አበበ አየለ ማሞ ሳህሌ ደጋጎ ክፍሌ አቦቸር ከመሳሰሉት የክብር ዘበኛ እና የፖሊስ ኦርኬስትራዎች
ተቀብሎ ሲያንቆረቁረው ሙዚቃው ከድምፅ አልፎ የሚዳሰስ ሕያው መንፈስ የመሆን አቅም ነበረው።
ዛሬ ላይ ሆኜ ያንን ትርኢት ሳስታውሰው ጥላሁን ለኢትዮጵያ ሙዚቃና ለኢትዮጵያዊነት ያለው ትርጉም ምን ያህል ጥልቅ ስሜት እንደሆነ አሁን ድረስ እንደ ህልም ይታየኛል ።
ያኔ መድረክ ላይ ሲወጣ የነበረው ግርማ ሞገስና ድምፁ ሲስተጋባ የተሰማኝ ስሜት ዛሬም ድረስ ዘፈኑን ስሰማው "የጦር ፊታውራሪ" የነበረ ጀግና ያህል ትዝ ይለኛል !!
ጥላሁን በመድረክ ላይ የነበረውን የበላይነት እና የሕዝብን ስሜት የመምራት ብቃቱን በሚገባ የመግለፅ አቅም ነበረው ።
ጥላሁን ዝም ብሎ ድምፃዊ ሳይሆን በዜማው የታጠቀ የሀገር መከታ ወታደርም ሆኖ እንደነበረ ማሳያ ነው ።
ለዚህ ነው የጥላሁን ገሠሠ የሀገር ፍቅር ዜማዎች ከጊዜና ከቦታ በላይ የሆኑ ናቸው የሚባሉት ። ለዚህም ነው ዛሬ ላይ ሆነን ስንሰማው የዛሬ 130 ዓመት በፊት የተነገረውን የዳግማዊ ምኒልክን የክተት አዋጅ የሚመስለን ።
ይህ የሚያሳየው ደግሞ ጥላሁን የኢትዮጵያን ታሪክ ኩራትና ነፃነት በድምፅ ቀርጾ ትውልድ እንዲወርሰው ማድረጉን ነው።
ወዳጆቼ
ስለ ጥላሁን ገሠሠ የሀገር ፍቅር ስሜት ስንናገር እነዚህ ሶስት መሰረታዊ እውነታዎች ጎልተው ይታያኛል ።
የቁርጠኝነት ድምፁን ስናደዳምጠው ጥላሁን "አገሬን" ሲል ዝም ብሎ ስም አይጠራም ለሀገሩ የሚሞትላትና የሚሰዋላት መሆኑን በቃናው ውስጥ ይሰማል። አጥንቴም ይከስከስ የሚለው ስንኝ ለዚህ ትልቅ ማሳያ ነው።
ጥላሁን ለሀገር ሲዘፍን መላው ኢትዮጵያዊ በአንድነት ቆሞ ፊታውራሪዬ ብሎ እንዲከተለው ያደርጋል።
ይህ ደግሞ በታሪካችን ውስጥ የታየ ትልቅ የጥበብ ተጽዕኖ ነው።
ከ130 ዓመት በፊት የነበረውን የአድዋ ጀግንነት ዛሬ ላለው ትውልድ በስሜት አገናኝቶ ማቅረብ የሚችለው እንደ ጥላሁን ያለ "የታሪክ ድልድይና የታሪክ ባለአደራ" ሲኖር ብቻ ነው።
እንኳንስ ደስታየን የሰውነቴን ሠው
እንኳን ነፃነቴን ፀጋ ክብሬን ትቸው
በናት አገር ምድር በሚያውቀኝ በማውቀው ...
ስቃይ መከራዬን ከአንችው ዘንድ ያድርገው ። የሚለው
ጥላሁን ለኢትዮጵያ የነበረውን ፍቅር ከምንም በላይ የሚያሳይ ነው። ከባዕድ አገር ደስታ ይልቅ የሀገሩን መከራ የመረጠበት የሞቱ አጋጣሚ ደግሞ ለሀገሩ ያለውን ፍቅር በደሙ ያረጋገጠበት ታላቅ ክስተት ነው ።
ጥላሁን ከአሜሪካ ተነስቶ ለፋሲካ በዓል ወደ ሀገሩ መግባቱና በዚያው ዕለት ማረፉ፣ "በሀገሬ አፈር ልቀበር" የሚለውን ጥልቅ የኢትዮጵያዊያን ምኞት የፈጸመበት ነው ይህ ቀረኝ የማይል የሚያሰኘው እስከ መጨረሻው ትንፋሹ ድረስ ከሀገሩና ከሕዝቡ ጋር መቆየቱ ነው ።
ሲሞት መላው የአዲስ አበባ ሕዝብ በነቂስ ወጥቶ አስከሬኑን ሲሸኜው ጥላሁን ለሕዝቡ የሰጠውን ፍቅር ሕዝቡ በታላቅ ክብር የመለሰለት መሆኑን ቅድስት ስላሴ ቤተክርስቲያን ህያው ምስክር ናት ። ያ ለቅሶ የአንድ ድምፃዊ ስንብት ሳይሆን የኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጅና የልብ ትርታ ሽኝት ነበር።
ጥላሁን በሕይወቱና በሞቱ ሀገርን መውደድ ማለት ትርጉሙን እስከ ሞት ድረስ መታመንን አረጋግጦበታል።
ሰውን መውደድ ! አብሮ ማልቀስና መቆም ሙያን መውደድ እስከ መጨረሻዋ ትንፋሽ ድረስ መዘመር ለኢትዮጵያዊያን ከድምፃዊነት በላይ የአንድነት ምልክት መሆን ነው።
እኔ በዓይኔ ያየሁትን በልቤ የሰነድኩትን ይህንን ታሪክ ለሚቀጥለው ትውልድ ሊተላለፍ የሚገባው የፍቅርና የሀገር አምልኮ ትልቅ ትምህርት ይሆናል ብየ ሳዘጋጀው ጥላሁን ገሠሠ
ትንፋሼ ተቀርፆ ይቀመጥ ማልቀሻ ይህ ነው የሞትኩለት የኔ ማስታወሻ
ታሪኬ ነው ድምፄ በማለት ያንጎራጎረው ሙዚቃ ከፍቼ እያዳመጥኩ ነበር።
ይህ ስንኝ ጥላሁን ገሠሠ አስቀድሞ በድምፁ የህይወቱ ታሪክ የሞቱ ማስታወሻ እና የሀገሩ ውበት መገለጫ እንደሚሆን ተረድቶት የተጫወተው ነበር ማለት ይቻላል ። ጥላሁን በጥቁርና ነጭ ወረቀት ላይ የሰፈረ ኑዛዜ ሳይሆን የተውልን በህይወት ቆሞ በዜማ የተናዘዘው ድንቅ ስንብት ነበረ ።
እነዚህ ስንኞች የጥላሁንን የጥበብ ክብርና ትህትና ሲገለፅበት እያዳመጥኩት ነበር ይህን ታሪክ የፃፍኩት ።
ወዳጃቸ
የጥላሁን ገሠሠ ድምፅ ዝም ብሎ የአየር ንዝረት አይደለም፤ ማንነቱ፣ ታሪኩና ለሀገሩ የከፈለው መስዋዕትነት ነው። በጩኸት መኖሬን ማለቱ ለሀገርና ለፍቅር ሲል ድምፁን እስከ መጨረሻው የጥገታ ነጥብ ድረስ መጠቀሙንና ለዚህም መሞቱን ያሳያል።
ድምፄን ሰምቶ ያዝናል ለረገፈው አፅሜ ሲል
እጅግ ልብ ይነካል !
ጥላሁን በከፍታው ላይ ሆኖ እንኳ ያስቀየምኩት ቢኖር ብሎ ይቅርታን ይጠይቃል። የሞተውን አፅሙን ሳይሆን የቀረውን ድምፁን ሰምተው ሰዎች እንዲያዝኑለትና ይቅር እንዲሉት መመኘቱ የሰው ልጅነቱንይቅርታና ትህትናውን
ፍርጥ አድርጎ ያሳያል።
ጥላሁን ገሠሠ በድምፁና በህይወቱ የሰራው ትልቁ ስራ ፍቅርንና ኢትዮጵያዊነትን ማዳን ነበር። ጥላሁን ከቀላል ስሜትነት አልፎ ሕይወት መስዋዕትነትና የሀገር ፍቅር ጥግ መሆኑን በሚገባ አስገንዝቦናል።ጥበብ እንዴት የአንድን ሕዝብ ወኔና ማንነት እንደምትቀርፅ ጥላሁን ትልቅ ማሳያ ነው።
ፍቅር ተግባር ነው ፍቅር ዝም ብሎ የሚሰማን ስሜት ሳይሆን እንደ ጥላሁን ዜማዎች ራስን አሳልፎ እስከ መስጠት የሚደርስ ውሳኔ መሆኑን መረዳት ከባድ አይደለም ።
ጥላሁን ገሰሰ የሚዘፈነው ለጆሮ ብቻ ሳይሆን ለህሊና እና ለነፍስ ጭምር ይመስለኛል ።
ጥላሁን ዛሬ በሥጋ ቢለየንም ታሪኬ ነው ድምፄ ብሎ እንደተናዘዘው ሁሉ ዛሬም በየልባችን ውስጥ ንጉሥ ሆኖ ይኖራል።እሱ ለሀገር ብቻ ሳይሆን ለሰው ልጅ ስቃይ የሚራራ የህሊና ድምፅ ነበረው።
የሀገር ፍቅር ለአፈርና ለሰንደቅ ዓላማ የሚከፈል የአጥንትና የደም መስዋዕትነት ሲሆን ጥላሁን ገሠሠ በስጋ ቢለየንም ያ በሕይወት ያለ ሐውልት ግን በዜማዎቹ ውስጥ ሁሌም አዲስ ሆኖ ይኖራል።
ባጭሩ የጥላሁን መሞት ዝም ብሎ የአንድ ድምፃዊ ማለፍ ብቻ አልነበረም የአንድ ዘመን መቋጫ የአንድ ትልቅ ተስፋ መደብዘዝ እና በኢትዮጵያ ሰማይ ላይ የሚበራው የሙዚቃ ኮከብ ወድቆ ሲሰበር
ሰማይ ባዶ የሆነ ያህል ተሰምቶናል።
ጥላሁን ገሠሠ በደስታ ጊዜ አብሮን የሚጨፍር በጦርነት ጊዜ ፊታውራሪ ሆኖ የሚያዘምት በረሃብና በችግር ጊዜ ደግሞ አብሮን የሚላቀስ የሕዝብ ልብ ነበር ።
ጥላሁንን ከአቅም በላይ ያደረገው ይሄው ሁለንተናዊነቱ ነው። ለፍቅር ለሀገርና ለሰብአዊነት የነበረው ጽናት እሱ ሞቶም እንዲኖር አድርጎታል።
የጥላሁን ገሠሠ ዘፈኖች "ኢትዮጵያዊ ስነ-ሰብዕና" የሚባል የፍልስፍና ዘርፍ ቢኖር የዛ ዘርፍ ዋና መማሪያ መፅሐፍ ይሆኑ ነበር ።ብቻ
የጥላሁንገሰሰ ሕይወት ልክ እንደ አንድ የተቀደሰ መፅሐፍ በመሆኑ እራሡ ከፍቶ እራሱ ዘግቶት አልፏል ።
ለዚህ ታላቅ ድምፃዊ በተወለደበት ከተማ አዲስ አበባ ላይ ዘላለማዊ ምልክት ሆኖ እንዲቀመጥ ሐውልቱ ስለቆመለት ደስታዬ ወደር የለውም ።
ነፍስ ይማር !!
5 months ago
AI የሰው ልጅን ከሥራ አያፈናቅልም፤ ይልቁንም አቅምን ያሳድጋል!
#ብዙዎቻችን "አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ (AI) ሥራዬን ይነጥቀኝ ይሆን?" የሚል ስጋት ነበረብን። ሆኖም የጆንስ ሆፕኪንስ ዩኒቨርሲቲ ያወጣው አዲስ ጥናት ይህንን ስጋት የሚቀይር አስገራሚ ውጤት ይፋ አድርጓል።
AIን መጠቀም የሚያስገኘው ትርፍ በቁጥር፦
ጥናቱ AIን በሥራቸው ላይ የጨመሩ ሠራተኞች ካልተጠቀሙት በተሻለ የሚከተሉትን ለውጦች እንዳሳዩ አረጋግጧል፦
የፈጠራ ችሎታ (Creativity)፦ በ 40% ጨምሯል!
የሥራ ፍጥነት (Efficiency)፦ በ 25% አድጓል!
የሥራ ጥራት (Quality)፦ በ 18% መሻሻል አሳይቷል!
AI አድካሚና ተደጋጋሚ ሥራዎችን በፍጥነት ቢሰራም፣ የሚከተሉት የሰው ልጅ ተፈጥሯዊ ክህሎቶች ግን በማሽኖች ሊተኩ እንደማይችሉ ጥናቱ ይገልጻል፦
ሂሳዊ አስተሳሰብ (Critical Thinking)
ሥነ-ምግባራዊ ውሳኔ አሰጣጥ (Ethics)
ጥልቅ ስሜታዊ ግንኙነት (Emotional Intelligence)
እንደ ዓለም ኢኮኖሚክ ፎረም (WEF) ትንበያ፣ በቴክኖሎጂው ምክንያት አንዳንድ ነባር ሥራዎች ቢቀየሩም፣ 97 ሚሊዮን የሚደርሱ አዳዲስና ዘመናዊ የሥራ ዕድሎች ይፈጠራሉ። ቁልፉ ያለው ራስን ከቴክኖሎጂው ጋር በማላመድና አዳዲስ ዲጂታል ክህሎቶችን በማዳበር ላይ ነው።
AIን በዕለት ተዕለት ሥራዎ ወይም ትምህርትዎ ላይ መጠቀም ጀምረዋል? የሥራ ጫናዎን ቀንሶልዎታል ወይስ ይበልጥ አሳስቦዎታል? ራስዎን ለነገው የሥራ ገበያ እንዴት እያዘጋጁ ነው?
#artificialintelligence #ai #futureofwork #technology #productivity #digitaltransformation #innovation #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን
#ብዙዎቻችን "አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ (AI) ሥራዬን ይነጥቀኝ ይሆን?" የሚል ስጋት ነበረብን። ሆኖም የጆንስ ሆፕኪንስ ዩኒቨርሲቲ ያወጣው አዲስ ጥናት ይህንን ስጋት የሚቀይር አስገራሚ ውጤት ይፋ አድርጓል።
AIን መጠቀም የሚያስገኘው ትርፍ በቁጥር፦
ጥናቱ AIን በሥራቸው ላይ የጨመሩ ሠራተኞች ካልተጠቀሙት በተሻለ የሚከተሉትን ለውጦች እንዳሳዩ አረጋግጧል፦
የፈጠራ ችሎታ (Creativity)፦ በ 40% ጨምሯል!
የሥራ ፍጥነት (Efficiency)፦ በ 25% አድጓል!
የሥራ ጥራት (Quality)፦ በ 18% መሻሻል አሳይቷል!
AI አድካሚና ተደጋጋሚ ሥራዎችን በፍጥነት ቢሰራም፣ የሚከተሉት የሰው ልጅ ተፈጥሯዊ ክህሎቶች ግን በማሽኖች ሊተኩ እንደማይችሉ ጥናቱ ይገልጻል፦
ሂሳዊ አስተሳሰብ (Critical Thinking)
ሥነ-ምግባራዊ ውሳኔ አሰጣጥ (Ethics)
ጥልቅ ስሜታዊ ግንኙነት (Emotional Intelligence)
እንደ ዓለም ኢኮኖሚክ ፎረም (WEF) ትንበያ፣ በቴክኖሎጂው ምክንያት አንዳንድ ነባር ሥራዎች ቢቀየሩም፣ 97 ሚሊዮን የሚደርሱ አዳዲስና ዘመናዊ የሥራ ዕድሎች ይፈጠራሉ። ቁልፉ ያለው ራስን ከቴክኖሎጂው ጋር በማላመድና አዳዲስ ዲጂታል ክህሎቶችን በማዳበር ላይ ነው።
AIን በዕለት ተዕለት ሥራዎ ወይም ትምህርትዎ ላይ መጠቀም ጀምረዋል? የሥራ ጫናዎን ቀንሶልዎታል ወይስ ይበልጥ አሳስቦዎታል? ራስዎን ለነገው የሥራ ገበያ እንዴት እያዘጋጁ ነው?
#artificialintelligence #ai #futureofwork #technology #productivity #digitaltransformation #innovation #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን
6 months ago
በስሜታችሁ ላይ ብቻ አትመኩ!
ብዙዎቻችን "ልብህ የሚልህን ስማ" የሚለውን ምክር እንደ ወርቅ እንቆጥረዋለን። ግን ስነ-ልቦና ባለሙያው ሳቻ ባቺም በአዲሱ መጽሐፉ ላይ እንደሚለው ከሆነ፣ ስሜቶቻችን ሁልጊዜ እውነተኞች አይደሉም፤ አንዳንዴም ክፉኛ ያታልሉናል።
ስለ ስነ-ልቦና የምናምናቸውን 4 የተሳሳቱ አመለካከቶች እስቲ እንያቸው፡
"ስሜት አይዋሽም"
ለምሳሌ አስፈሪ ፊልም ስታዩ ልባችሁ ይመታል፣ ትፈራላችሁ። ምንም እንኳን አደጋ እንደሌለ ብታውቁም ስሜታችሁ ግን "አደጋ አለ" ይላችኋል። ስሜት እንደ አየር ሁኔታ ተለዋዋጭ ስለሆነ ሁልጊዜ እውነት ነው ብላችሁ አትደምድሙ።
መፍትሄ፡ የሚሰማችሁን ስሜትና ምክንያቱን ለይታችሁ እወቁ። "አሁን የሚሰማኝ ፍርሃት/ጭንቀት ከእውነታው ጋር ይገጥማል?" ብላችሁ ራሳችሁን ጠይቁ።
2. "ውጥረት ስራ ያቀላጥፋል"
አንዳንዴ ለጥቂት ጊዜ መወጠር ንቁ ሊያደርገን ይችላል። ነገር ግን "ውጥረት ውስጥ ስሆን በደንብ እሰራለሁ" ብሎ ማመን ስህተት ነው። በሂደት አቅማችን እንዲደክም እና እንድንዝል ያደርገናል።
መፍትሄ፡ ከመጠን በላይ መልፋት ውጤታማ እንደማያደርግ ተረድታችሁ፣ አቅማችሁ ሲዝል እረፍት ውሰዱ።
3. "መጨነቅ አስፈላጊ ነው"
ስለ ነገው አየር ንብረትም ይሁን ስለ ጤናችን መጨነቅ ውጤቱን አይለውጠውም። እንዲያውም አብዛኛው የምንጨነቅላቸው ነገሮች በጭራሽ አይከሰቱም።
መፍትሄ፡ "የጭንቀት ጊዜ" መድቡ (ለምሳሌ በቀን 15 ደቂቃ)። ከዚያ ውጭ ጭንቀት ሲመጣ "አቁም!" በማለት ለሌላ ስራ ትኩረት ስጡ።
4. "ሁኔታዎችን መቀበል እጅ መስጠት ነው"
የማይለወጥን ነገር (ለምሳሌ የፍቅር ግንኙነት ማብቃቱን ወይም አቅምህን የሚበልጥ ስራን) አምኖ መቀበል መሸነፍ አይደለም። ይልቁንም ለውስጥ ሰላም እና ወደፊት ለመራመድ ትልቁ መንገድ ነው።
ማጠቃለያ፡ ስሜታችሁን መርምሩ እንጂ በጭፍን አትከተሉት!
👉ይህ ጽሁፍ የተወሰደው "The Truth About Feelings" (በጀርመንኛ "Gefühle sind keine Tatsachen") ከተሰኘው የስነ-ልቦና ባለሙያው ሳቻ ባቺም መጽሐፍ ነው።
ብዙዎቻችን "ልብህ የሚልህን ስማ" የሚለውን ምክር እንደ ወርቅ እንቆጥረዋለን። ግን ስነ-ልቦና ባለሙያው ሳቻ ባቺም በአዲሱ መጽሐፉ ላይ እንደሚለው ከሆነ፣ ስሜቶቻችን ሁልጊዜ እውነተኞች አይደሉም፤ አንዳንዴም ክፉኛ ያታልሉናል።
ስለ ስነ-ልቦና የምናምናቸውን 4 የተሳሳቱ አመለካከቶች እስቲ እንያቸው፡
"ስሜት አይዋሽም"
ለምሳሌ አስፈሪ ፊልም ስታዩ ልባችሁ ይመታል፣ ትፈራላችሁ። ምንም እንኳን አደጋ እንደሌለ ብታውቁም ስሜታችሁ ግን "አደጋ አለ" ይላችኋል። ስሜት እንደ አየር ሁኔታ ተለዋዋጭ ስለሆነ ሁልጊዜ እውነት ነው ብላችሁ አትደምድሙ።
መፍትሄ፡ የሚሰማችሁን ስሜትና ምክንያቱን ለይታችሁ እወቁ። "አሁን የሚሰማኝ ፍርሃት/ጭንቀት ከእውነታው ጋር ይገጥማል?" ብላችሁ ራሳችሁን ጠይቁ።
2. "ውጥረት ስራ ያቀላጥፋል"
አንዳንዴ ለጥቂት ጊዜ መወጠር ንቁ ሊያደርገን ይችላል። ነገር ግን "ውጥረት ውስጥ ስሆን በደንብ እሰራለሁ" ብሎ ማመን ስህተት ነው። በሂደት አቅማችን እንዲደክም እና እንድንዝል ያደርገናል።
መፍትሄ፡ ከመጠን በላይ መልፋት ውጤታማ እንደማያደርግ ተረድታችሁ፣ አቅማችሁ ሲዝል እረፍት ውሰዱ።
3. "መጨነቅ አስፈላጊ ነው"
ስለ ነገው አየር ንብረትም ይሁን ስለ ጤናችን መጨነቅ ውጤቱን አይለውጠውም። እንዲያውም አብዛኛው የምንጨነቅላቸው ነገሮች በጭራሽ አይከሰቱም።
መፍትሄ፡ "የጭንቀት ጊዜ" መድቡ (ለምሳሌ በቀን 15 ደቂቃ)። ከዚያ ውጭ ጭንቀት ሲመጣ "አቁም!" በማለት ለሌላ ስራ ትኩረት ስጡ።
4. "ሁኔታዎችን መቀበል እጅ መስጠት ነው"
የማይለወጥን ነገር (ለምሳሌ የፍቅር ግንኙነት ማብቃቱን ወይም አቅምህን የሚበልጥ ስራን) አምኖ መቀበል መሸነፍ አይደለም። ይልቁንም ለውስጥ ሰላም እና ወደፊት ለመራመድ ትልቁ መንገድ ነው።
ማጠቃለያ፡ ስሜታችሁን መርምሩ እንጂ በጭፍን አትከተሉት!
👉ይህ ጽሁፍ የተወሰደው "The Truth About Feelings" (በጀርመንኛ "Gefühle sind keine Tatsachen") ከተሰኘው የስነ-ልቦና ባለሙያው ሳቻ ባቺም መጽሐፍ ነው።
6 months ago
የትዝታ እስረኞች፡ የቀድሞ ፍቅረኛን ለመርሳት ሳይንሱ ምን ይላል?
ፍቅር ሲያበቃ፣ ታሪኩ የሚያበቃው በመጽሐፉ የመጨረሻ ገጽ ላይ ሳይሆን በሰውየው የልብ ምትና በአእምሮው ትውስታ ውስጥ ነው። "ጊዜ ሁሉንም ቁስል ይፈውሳል" የሚለው ብርቅዬ አባባል በብዙዎቻችን ዘንድ ቢዘወተርም፣ ሳይንሱ ግን "ጊዜ ብቻውን በቂ አይደለም" ይለናል። በቅርቡ በመቶዎች በሚቆጠሩ ሰዎች ላይ የተደረገ ጥናት፣ አንድን የቀድሞ ፍቅረኛ እንደ ተራ ሰው ለማየትና ከትዝታው ለማገገም የሚፈጀውን እውነተኛ የጊዜ ሰሌዳ ይፋ አድርጓል።
1. የ4.18 ዓመታት ጉዞ፡ የልብ ቁስል ሳይንሳዊ ስሌት
ብዙዎቻችን ጥቂት ወራትን ወይንም አንድ ዓመትን እንደ መደበኛ የማገገሚያ ጊዜ ብንወስድም፣ የጂያ ዋይ ቾንግ እና አር.ሲ ፍሬሊ ጥናት ግን አስገራሚ ውጤት ይዞ መጥቷል። እንደ ጥናቱ ከሆነ፣ አንድ ሰው የቀድሞ አጋሩን እንደ ማንኛውም ተራ የቀድሞ የሚያውቀው ሰው (Ordinary acquaintance) ለማየት በአማካይ 4.18 ዓመታት ይፈጅበታል።
ይህ ማለት ስሜቱ በአንድ ጀምበር አይጠፋም፤ ይልቁንም እንደ ሻማ ቀስ በቀስ እየቀነሰ የሚሄድ ሂደት ነው። ይህ ረጅም ጊዜ የሚያሳየው፣ የሰው ልጅ አእምሮ ለፍቅር ትስስር የሚሰጠው ዋጋ ምን ያህል ጥልቅ እንደሆነና በአጭር ጊዜ ሊገነጠል የማይችል የነርቭ ትስስር እንደሚፈጥር ነው።
2. ስሜታዊ ትስስር ሙሉ በሙሉ ይጠፋል?
በሳይንቲስቶች መካከል ለዓመታት ሲያከራክር የነበረው ነጥብ "የቀድሞ አጋሮች ከእኛ ጋር ይቆያሉ ወይስ በሂደት ይጠፋሉ?" የሚለው ነበር። ጥናቱ ሁለት መላምቶችን መርምሯል፡-
የመጀመሪያው እይታ፡ ምንም እንኳን ግንኙነቱ ቢያበቃም፣ የቀድሞ አጋር በውስጣችን የሆነ ቦታ ሆኖ ስሜታዊ ፍላጎታችንን ማሟላቱን ይቀጥላል።
ሁለተኛው እይታ፡ ጊዜ እያለፈ ሲሄድ ትስስሩ ሙሉ በሙሉ ይበጠሳል፤ ግለሰቡም ወደ ነባር ትውስታነት ይቀየራል።
የጥናቱ ውጤት የሚያሳየው ሁለተኛው እይታ ይበልጥ ሚዛን እንደሚደፋ ነው። አዎ፣ ጊዜ እያለፈ ሲሄድ ያ ከባድ ትስስር ይላላል። ነገር ግን ይህ የሚሆነው ግንኙነቱን ሙሉ በሙሉ ለመቁረጥ በምናደርገው ጥረት ላይ ተመስርቶ ነው።
3. ሂደቱን የሚያጓትቱ መሰናክሎች
ሳይንሱ ለምን የተወሰኑ ሰዎች ፈጥነው እንደሚረሱ፣ ሌሎች ግን ለዓመታት በትዝታ እንደሚማቅቁ ግልጽ ማብራሪያ ይሰጣል። ለዚህም ዋናው ምክንያት "የአባሪነት ዘይቤ" (Attachment Style) ነው።
ጭንቀት የበዛበት አባሪነት (Anxious Attachment)፦ እነዚህ ሰዎች የመተው ፍርሃት ያለባቸው በመሆኑ፣ ግንኙነቱ ካለቀ በኋላም አእምሮአቸው የቀድሞ አጋራቸውን እንደ ደህንነት መጠለያ አድርጎ ያስባል። በዚህም ምክንያት የ4 ዓመቱ ጉዞ ወደ 10 ዓመት ሊራዘም ይችላል።
የመግባቢያ ድልድዮች አለመፍረስ፦ ግንኙነቱ ካለቀ በኋላም "ጓደኛ እንሁን" በሚል ሰበብ መልዕክት መለዋወጥ፣ ማህበራዊ ሚዲያቸውን መከታተል (Stalking) ወይም አልፎ አልፎ መገናኘት ሂደቱን በከፍተኛ ሁኔታ ያዘገየዋል። እያንዳንዱ አዲስ ግንኙነት አሮጌውን ቁስል መልሶ እንደሚፈታ የሳይንስ ሊቃውንቱ ያስጠነቅቃሉ።
4. መደምደሚያ፡ የልብን ቁስል እንዴት እንፈውስ?
የ4.18 ዓመታት ስሌት ለብዙዎቻችን ተስፋ አስቆራጭ ሊመስል ይችላል። ሆኖም ይህ ማለት ለ4 ዓመታት እናለቅሳለን ማለት አይደለም። ይልቁንም ስሜቱ ቀስ በቀስ እየቀነሰ መጥቶ፣ በመጨረሻው መስመር ላይ ግለሰቡን ስናየው ምንም ዓይነት የልብ ትርታ ሳይሰማን የምንቀጥልበት ደረጃ ላይ እንደርሳለን ማለት ነው።
ትዝታን ለመርሳት የግድ "አእምሮን ማጠብ" አያስፈልግም፤ ይልቁንም ለአዲስ ትዝታዎች ቦታ መስጠትና ከቀድሞው ጋር ያለን የአካልም ሆነ የዲጂታል ግንኙነት መቁረጥ ብቸኛው ፈጣን መንገድ ነው።
ፍቅር ሲያበቃ፣ ታሪኩ የሚያበቃው በመጽሐፉ የመጨረሻ ገጽ ላይ ሳይሆን በሰውየው የልብ ምትና በአእምሮው ትውስታ ውስጥ ነው። "ጊዜ ሁሉንም ቁስል ይፈውሳል" የሚለው ብርቅዬ አባባል በብዙዎቻችን ዘንድ ቢዘወተርም፣ ሳይንሱ ግን "ጊዜ ብቻውን በቂ አይደለም" ይለናል። በቅርቡ በመቶዎች በሚቆጠሩ ሰዎች ላይ የተደረገ ጥናት፣ አንድን የቀድሞ ፍቅረኛ እንደ ተራ ሰው ለማየትና ከትዝታው ለማገገም የሚፈጀውን እውነተኛ የጊዜ ሰሌዳ ይፋ አድርጓል።
1. የ4.18 ዓመታት ጉዞ፡ የልብ ቁስል ሳይንሳዊ ስሌት
ብዙዎቻችን ጥቂት ወራትን ወይንም አንድ ዓመትን እንደ መደበኛ የማገገሚያ ጊዜ ብንወስድም፣ የጂያ ዋይ ቾንግ እና አር.ሲ ፍሬሊ ጥናት ግን አስገራሚ ውጤት ይዞ መጥቷል። እንደ ጥናቱ ከሆነ፣ አንድ ሰው የቀድሞ አጋሩን እንደ ማንኛውም ተራ የቀድሞ የሚያውቀው ሰው (Ordinary acquaintance) ለማየት በአማካይ 4.18 ዓመታት ይፈጅበታል።
ይህ ማለት ስሜቱ በአንድ ጀምበር አይጠፋም፤ ይልቁንም እንደ ሻማ ቀስ በቀስ እየቀነሰ የሚሄድ ሂደት ነው። ይህ ረጅም ጊዜ የሚያሳየው፣ የሰው ልጅ አእምሮ ለፍቅር ትስስር የሚሰጠው ዋጋ ምን ያህል ጥልቅ እንደሆነና በአጭር ጊዜ ሊገነጠል የማይችል የነርቭ ትስስር እንደሚፈጥር ነው።
2. ስሜታዊ ትስስር ሙሉ በሙሉ ይጠፋል?
በሳይንቲስቶች መካከል ለዓመታት ሲያከራክር የነበረው ነጥብ "የቀድሞ አጋሮች ከእኛ ጋር ይቆያሉ ወይስ በሂደት ይጠፋሉ?" የሚለው ነበር። ጥናቱ ሁለት መላምቶችን መርምሯል፡-
የመጀመሪያው እይታ፡ ምንም እንኳን ግንኙነቱ ቢያበቃም፣ የቀድሞ አጋር በውስጣችን የሆነ ቦታ ሆኖ ስሜታዊ ፍላጎታችንን ማሟላቱን ይቀጥላል።
ሁለተኛው እይታ፡ ጊዜ እያለፈ ሲሄድ ትስስሩ ሙሉ በሙሉ ይበጠሳል፤ ግለሰቡም ወደ ነባር ትውስታነት ይቀየራል።
የጥናቱ ውጤት የሚያሳየው ሁለተኛው እይታ ይበልጥ ሚዛን እንደሚደፋ ነው። አዎ፣ ጊዜ እያለፈ ሲሄድ ያ ከባድ ትስስር ይላላል። ነገር ግን ይህ የሚሆነው ግንኙነቱን ሙሉ በሙሉ ለመቁረጥ በምናደርገው ጥረት ላይ ተመስርቶ ነው።
3. ሂደቱን የሚያጓትቱ መሰናክሎች
ሳይንሱ ለምን የተወሰኑ ሰዎች ፈጥነው እንደሚረሱ፣ ሌሎች ግን ለዓመታት በትዝታ እንደሚማቅቁ ግልጽ ማብራሪያ ይሰጣል። ለዚህም ዋናው ምክንያት "የአባሪነት ዘይቤ" (Attachment Style) ነው።
ጭንቀት የበዛበት አባሪነት (Anxious Attachment)፦ እነዚህ ሰዎች የመተው ፍርሃት ያለባቸው በመሆኑ፣ ግንኙነቱ ካለቀ በኋላም አእምሮአቸው የቀድሞ አጋራቸውን እንደ ደህንነት መጠለያ አድርጎ ያስባል። በዚህም ምክንያት የ4 ዓመቱ ጉዞ ወደ 10 ዓመት ሊራዘም ይችላል።
የመግባቢያ ድልድዮች አለመፍረስ፦ ግንኙነቱ ካለቀ በኋላም "ጓደኛ እንሁን" በሚል ሰበብ መልዕክት መለዋወጥ፣ ማህበራዊ ሚዲያቸውን መከታተል (Stalking) ወይም አልፎ አልፎ መገናኘት ሂደቱን በከፍተኛ ሁኔታ ያዘገየዋል። እያንዳንዱ አዲስ ግንኙነት አሮጌውን ቁስል መልሶ እንደሚፈታ የሳይንስ ሊቃውንቱ ያስጠነቅቃሉ።
4. መደምደሚያ፡ የልብን ቁስል እንዴት እንፈውስ?
የ4.18 ዓመታት ስሌት ለብዙዎቻችን ተስፋ አስቆራጭ ሊመስል ይችላል። ሆኖም ይህ ማለት ለ4 ዓመታት እናለቅሳለን ማለት አይደለም። ይልቁንም ስሜቱ ቀስ በቀስ እየቀነሰ መጥቶ፣ በመጨረሻው መስመር ላይ ግለሰቡን ስናየው ምንም ዓይነት የልብ ትርታ ሳይሰማን የምንቀጥልበት ደረጃ ላይ እንደርሳለን ማለት ነው።
ትዝታን ለመርሳት የግድ "አእምሮን ማጠብ" አያስፈልግም፤ ይልቁንም ለአዲስ ትዝታዎች ቦታ መስጠትና ከቀድሞው ጋር ያለን የአካልም ሆነ የዲጂታል ግንኙነት መቁረጥ ብቸኛው ፈጣን መንገድ ነው።
Sponsored by
Surafel
6 months ago
🛑 ክብደት ለመቀነስ ሲሉ እነዚህን ስህተቶች እየሰሩ ይሆን? 🛑
ብዙዎቻችን ክብደት ለመቀነስ ጥረት ብናደርግም፣ ሳናውቃቸው የምንሰራቸው ትናንሽ ስህተቶች ውጤቱን ያበላሹብናል። ባለሙያዎች የሚከተሉትን ስህተቶች እንድንጠነቀቅ ይመክራሉ፦
🥩 ፕሮቲን መቀነስ፦ ፕሮቲን የረሃብ ስሜት እንዳይሰማን ስለሚያደርግ፣ በምግባችን ውስጥ ካልተካተተ ቶሎ እንድንራብ ያደርጋል።
🥦 ፋይበር (Fiber) አለመውሰድ፦ ፋይበር ያላቸው ምግቦች ሆዳችን የሞላ እንዲመስለን በማድረግ ብዙ ከመብላት ይታደጉናል።
🍽️ ከሌላ ሰው ሰሃን 'መቅመስ'፦ "ትንሽ እኮ ናት" ብለን ከሌላ ሰው ሰሃን የምንወስዳቸው ምግቦች የካሎሪ ቁጥጥራችንን ያዛቡታል።
🥤 ከፍተኛ ካሎሪ ያላቸው መጠጦች፦ የፍራፍሬ ጭማቂዎች፣ በወተት የተበተሉ ቡናዎች እና ለስላሳ መጠጦች ሳናውቀው ከፍተኛ ካሎሪ ይጨምሩብናል።
🏋️ ስፖርት ላይ ክብደት አለማንሳት፦ በሩጫ ማሽን (Treadmill) ላይ ብቻ መሮጥ በቂ አይደለም፤ ክብደት ማንሳት ጡንቻን በማጠንከር የምግብ ስልቀጣን (Metabolism) ያፋጥናል።
🍕 የሳምንቱ መጨረሻ 'ቅጥ ያጣ' አመጋገብ፦ በስራ ቀናት ተቆጥበው ቅዳሜ እና እሁድ ከመጠን በላይ መብላት የሳምንቱን ልፋት ከንቱ ያደርገዋል።
⏰ የምግብ ሰዓት አለመጠበቅ፦ በተለይ ቁርስን ማሳለፍ ቀኑን ሙሉ ከፍተኛ ካሎሪ ያላቸውን ምግቦች እንድንመኝ ያደርገናል።
😴 እንቅልፍ ማጣት፦ በቂ እንቅልፍ አለማግኘት የረሃብ ሆርሞኖችን በማነቃቃት ለክብደት መጨመር ምክንያት ይሆናል።
🦠 የጨጓራ ጤናን መዘንጋት፦ በጨጓራና አንጀት ውስጥ ያሉ ጠቃሚ ባክቴሪያዎች መመጣጠን መጓደል ለክብደት መጨመር ይዳርጋል።
💡 ማጠቃለያ፦ ጤናማ ክብደት ለመቀነስ የተመጣጠነ ምግብ መመገብ፣ በቂ እንቅልፍ መተኛት እና ወጥ የሆነ ጥንቃቄ ማድረግ ወሳኝ ነው!
ብዙዎቻችን ክብደት ለመቀነስ ጥረት ብናደርግም፣ ሳናውቃቸው የምንሰራቸው ትናንሽ ስህተቶች ውጤቱን ያበላሹብናል። ባለሙያዎች የሚከተሉትን ስህተቶች እንድንጠነቀቅ ይመክራሉ፦
🥩 ፕሮቲን መቀነስ፦ ፕሮቲን የረሃብ ስሜት እንዳይሰማን ስለሚያደርግ፣ በምግባችን ውስጥ ካልተካተተ ቶሎ እንድንራብ ያደርጋል።
🥦 ፋይበር (Fiber) አለመውሰድ፦ ፋይበር ያላቸው ምግቦች ሆዳችን የሞላ እንዲመስለን በማድረግ ብዙ ከመብላት ይታደጉናል።
🍽️ ከሌላ ሰው ሰሃን 'መቅመስ'፦ "ትንሽ እኮ ናት" ብለን ከሌላ ሰው ሰሃን የምንወስዳቸው ምግቦች የካሎሪ ቁጥጥራችንን ያዛቡታል።
🥤 ከፍተኛ ካሎሪ ያላቸው መጠጦች፦ የፍራፍሬ ጭማቂዎች፣ በወተት የተበተሉ ቡናዎች እና ለስላሳ መጠጦች ሳናውቀው ከፍተኛ ካሎሪ ይጨምሩብናል።
🏋️ ስፖርት ላይ ክብደት አለማንሳት፦ በሩጫ ማሽን (Treadmill) ላይ ብቻ መሮጥ በቂ አይደለም፤ ክብደት ማንሳት ጡንቻን በማጠንከር የምግብ ስልቀጣን (Metabolism) ያፋጥናል።
🍕 የሳምንቱ መጨረሻ 'ቅጥ ያጣ' አመጋገብ፦ በስራ ቀናት ተቆጥበው ቅዳሜ እና እሁድ ከመጠን በላይ መብላት የሳምንቱን ልፋት ከንቱ ያደርገዋል።
⏰ የምግብ ሰዓት አለመጠበቅ፦ በተለይ ቁርስን ማሳለፍ ቀኑን ሙሉ ከፍተኛ ካሎሪ ያላቸውን ምግቦች እንድንመኝ ያደርገናል።
😴 እንቅልፍ ማጣት፦ በቂ እንቅልፍ አለማግኘት የረሃብ ሆርሞኖችን በማነቃቃት ለክብደት መጨመር ምክንያት ይሆናል።
🦠 የጨጓራ ጤናን መዘንጋት፦ በጨጓራና አንጀት ውስጥ ያሉ ጠቃሚ ባክቴሪያዎች መመጣጠን መጓደል ለክብደት መጨመር ይዳርጋል።
💡 ማጠቃለያ፦ ጤናማ ክብደት ለመቀነስ የተመጣጠነ ምግብ መመገብ፣ በቂ እንቅልፍ መተኛት እና ወጥ የሆነ ጥንቃቄ ማድረግ ወሳኝ ነው!
6 months ago
🛑 ከአባት ጋር ያለ ግንኙነት በፍቅር ህይወት ላይ ያለው ተፅዕኖ
ብዙዎቻችን "የአባት ፍቅር ማጣት" (Father Issues) የሚለውን ቃል በስፋት ስንሰማው እንቆያለን። ይህ ችግር በሰዎች ዘንድ የሚታየው ከአባታቸው ጋር የነበራቸው ግንኙነት የተቋረጠ፣ የሻከረ ወይም በበታችነት ስሜት የታጀበ ሲሆን ነው።
ጥናቶች እንደሚጠቁሙት፣ ከአባታችን ጋር የነበረን ግንኙነት አውቀንም ይሁን ሳናውቀው የትዳር ወይም የፍቅር አጋር ምርጫችንን ይወስነዋል። በተለይ የሚከተሉት 6 ምልክቶች የሚታዩባችሁ ከሆነ፣ ካልተፈወሰ የአባትና ልጅ ግንኙነት የመነጩ ሊሆኑ ይችላሉ፦
ስሜታቸውን ከማይገልጹ ሰዎች ጋር መውደቅ፦ ፍቅርንና ቅርርብን የሚፈሩ ሰዎችን የመምረጥ ዝንባሌ።
ውስብስብ የአባትነት ታሪክ፦ አባትየው በህይወት የሌለ፣ ጨካኝ፣ ወይም በጣም ተቺ ከነበረ በልጁ ስነ-ልቦና ላይ ትልቅ ጠባሳ ጥሎ ያልፋል።
ቁርጠኝነትን መፍራት (Fear of Commitment)፦ ግንኙነቱ እየጠነከረ ሲመጣ የመሸሽ፣ የመለየት ወይም ጥሎ የመጥፋት ስሜት።
የእምነት ማጣት፦ አጋርን ሁልጊዜ መጠራጠር እና የገባውን ቃል አይጠብቅም ብሎ መስጋት።
ለግኑኝነት ከመጠን በላይ መልፋት፦ የራሳቸውን ፍላጎት መስዋዕት በማድረግ ግንኙነቱ ብቻ እንዳይበተን ብቻቸውን መታገልና መለማመጥ።
ጤናማ ግንኙነትን ማበላሸት (Sabotaging)፦ ግንኙነቱ ሰላማዊ ሲሆን "አንድ ችግር መፈጠሩ አይቀርም" በሚል ስጋት ሆን ብሎ ጠብ መጫር ወይም ግንኙነቱን ማበላሸት።
ማጠቃለያ፦
እነዚህን ስር የሰደዱ ልማዶች መረዳት ለተሻለ የፍቅር ህይወት እና ለውስጥ ሰላም የመጀመሪያው እርምጃ ነው። ራስን መፈተሽና አስፈላጊ ከሆነም የባለሙያ ምክር ማግኘት ነገን ብሩህ ያደርገዋል።
💬 እናንተስ በዚህ ዙሪያ ምን ትላላችሁ? አስተያየታችሁን በኮመንት አጋሩን።
ብዙዎቻችን "የአባት ፍቅር ማጣት" (Father Issues) የሚለውን ቃል በስፋት ስንሰማው እንቆያለን። ይህ ችግር በሰዎች ዘንድ የሚታየው ከአባታቸው ጋር የነበራቸው ግንኙነት የተቋረጠ፣ የሻከረ ወይም በበታችነት ስሜት የታጀበ ሲሆን ነው።
ጥናቶች እንደሚጠቁሙት፣ ከአባታችን ጋር የነበረን ግንኙነት አውቀንም ይሁን ሳናውቀው የትዳር ወይም የፍቅር አጋር ምርጫችንን ይወስነዋል። በተለይ የሚከተሉት 6 ምልክቶች የሚታዩባችሁ ከሆነ፣ ካልተፈወሰ የአባትና ልጅ ግንኙነት የመነጩ ሊሆኑ ይችላሉ፦
ስሜታቸውን ከማይገልጹ ሰዎች ጋር መውደቅ፦ ፍቅርንና ቅርርብን የሚፈሩ ሰዎችን የመምረጥ ዝንባሌ።
ውስብስብ የአባትነት ታሪክ፦ አባትየው በህይወት የሌለ፣ ጨካኝ፣ ወይም በጣም ተቺ ከነበረ በልጁ ስነ-ልቦና ላይ ትልቅ ጠባሳ ጥሎ ያልፋል።
ቁርጠኝነትን መፍራት (Fear of Commitment)፦ ግንኙነቱ እየጠነከረ ሲመጣ የመሸሽ፣ የመለየት ወይም ጥሎ የመጥፋት ስሜት።
የእምነት ማጣት፦ አጋርን ሁልጊዜ መጠራጠር እና የገባውን ቃል አይጠብቅም ብሎ መስጋት።
ለግኑኝነት ከመጠን በላይ መልፋት፦ የራሳቸውን ፍላጎት መስዋዕት በማድረግ ግንኙነቱ ብቻ እንዳይበተን ብቻቸውን መታገልና መለማመጥ።
ጤናማ ግንኙነትን ማበላሸት (Sabotaging)፦ ግንኙነቱ ሰላማዊ ሲሆን "አንድ ችግር መፈጠሩ አይቀርም" በሚል ስጋት ሆን ብሎ ጠብ መጫር ወይም ግንኙነቱን ማበላሸት።
ማጠቃለያ፦
እነዚህን ስር የሰደዱ ልማዶች መረዳት ለተሻለ የፍቅር ህይወት እና ለውስጥ ሰላም የመጀመሪያው እርምጃ ነው። ራስን መፈተሽና አስፈላጊ ከሆነም የባለሙያ ምክር ማግኘት ነገን ብሩህ ያደርገዋል።
💬 እናንተስ በዚህ ዙሪያ ምን ትላላችሁ? አስተያየታችሁን በኮመንት አጋሩን።
6 months ago
አምስት ደቂቃ ዛሬ፦ ለነገዋ ውድ ሕይወትዎ
በአገራችን ኢትዮጵያ "ጤና ይስጥልኝ" ብለን ሰላምታ መለዋወጥ የተለመደ ቢሆንም፣ ዛሬ ግን ያ ጤና በቤታችን እና በቢሯችን ውስጥ በሚገኙ ምቹ ወንበሮች፣ በሞባይል ስልኮች እና በቴክኖሎጂ ምቾት እየተሰረቀ ይገኛል። በኢትዮጵያ የሕዝብ ጤና ኢንስቲትዩት (EPHI) ጥናቶች እንደሚያሳዩት፣ ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎች (እንደ የደም ግፊት፣ ስኳር እና የልብ በሽታ) በኢትዮጵያ ለሚከሰቱት ሞቶች ከ40% በላይ ድርሻ ይይዛሉ። ይህ አሀዝ በየዓመቱ በአሰቃቂ ሁኔታ እየጨመረ ነው።
የዝምታው ገዳይ ድምፅ
ብዙዎቻችን ቀኑን ሙሉ ተቀምጠን እንውላለን። በቢሮ ውስጥ ከኮምፒውተር ፊት፣ በትራንስፖርት መጨናነቅ ውስጥ በታክሲ ወንበር ላይ፣ ማታ ደግሞ ከቴሌቪዥን ፊት። ይህ "ተቀምጦ የመዋል" (Sedentary Lifestyle) አባዜ በኢትዮጵያውያን ዘንድ አዲስ እና አደገኛ ስጋት ሆኗል።
ጥናቶች እንደሚጠቁሙት በቀን ውስጥ ከ7-8 ሰዓታት በላይ መቀመጥ፣ ሰውነታችን "ተኝቻለሁ" ብሎ እንዲያስብ ያደርገዋል። በዚህ ጊዜ የደም ዝውውር ይገታል፣ ስኳርን የማቃጠል አቅማችን ይቀንሳል፣ ደም ስሮቻችንም መጥበብ ይጀምራሉ። ውጤቱም፦
የልብ ድካም፦ በድንገት የሚመጣና ቤተሰብን የሚበትን።
የስኳር በሽታ፦ ለዘላለም ከመድኃኒት ጋር የሚያቆራኝ።
የአእምሮ ጭንቀት፦ በብቸኝነት እና በድካም ስሜት የታጀበ።
የአምስት ደቂቃ ተዓምር (Brisk Walk)
ብዙዎቻችን የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ለማድረግ ውድ የጂም (Gym) ክፍያ ወይም ረጅም ሰዓት እንደሚያስፈልግ እናስባለን። ነገር ግን ሳይንሳዊ ጥናቶች የሚያረጋግጡት እውነት ሌላ ነው።
በየቀኑ ለ5 ደቂቃ ብቻ ፈጠን ያለ እርምጃ (Brisk Walk) መራመድ የሞት አደጋን በከፍተኛ ሁኔታ ይቀንሳል። ይህ እርምጃ ተራ እርምጃ ሳይሆን፣ ልብ ትርታዋ ትንሽ ከፍ የሚልበት፣ ነገር ግን ትንፋሽ የማይቆርጥ መሆን አለበት።
"አምስት ደቂቃ ለጤናማ ሰው አጭር ጊዜ ልትሆን ትችላለች፤ ለታመመ ሰው ግን አምስት ደቂቃ ሙሉ ሕይወቱ ናት።"
በኢትዮጵያዊ ሕይወት ውስጥ እንዴት እንተግብረው?
ይህንን ለውጥ ለማምጣት የግድ የአትሌት ትጥቅ አያስፈልግዎትም፦
ታክሲ ቀድመው ይውረዱ፦ መድረሻዎ ላይ ከመድረስዎ አንድ ፌርማታ ቀድመው በመውረድ ያቺን 5 ደቂቃ በፈጣን እርምጃ ይጓዙ።
ሊፍት ይተዉ፦ በህንፃዎች ላይ በሊፍት ፈንታ ደረጃን ይጠቀሙ።
የስልክ ወሬ በእግር፦ በስልክ ሲያወሩ ቁጭ ብለው ሳይሆን በቤትዎ ወይም በቢሮዎ ውስጥ በመመላለስ ይሁን።
የሻይ ሰዓት፦ በሻይ ዕረፍትዎ ወቅት ቁጭ ብለው ከማውራት፣ ሻይዎ እስኪመጣ ድረስ ለጥቂት ደቂቃዎች ወጣ ብለው ይንቀሳቀሱ።
አሳዛኙ እውነት እና ተስፋው
ዛሬ በኢትዮጵያ ሆስፒታሎች ውስጥ የምናያቸው ብዙዎቹ ወጣቶችና አዋቂዎች፣ "ኧረ በጊዜ በትንሹ በተንቀሳቀስኩ ኖሮ" ብለው የሚቆጩ ናቸው። የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ማጣት ጡንቻን ያደክማል፣ አጥንትን ያሳሳል፣ በመጨረሻም በሰው እጅ እንድንጠበቅ ያደርገናል።
ነገር ግን ተስፋ አለ! ያቺ ዛሬ የምትጀምሯት 5 ደቂቃ፣ ነገ ከልጆችዎ ጋር በደስታ የመጫወት ዕድልን ትሰጥዎታለች። ዛሬ የሚወሰድ አንድ እርምጃ፣ ነገ ሊመጣ ከሚችል የድንገተኛ ህመም እና የሕክምና ወጪ ይታደግዎታል።
ውድ አንባቢያን፦
ሕይወት በአምስት ደቂቃ ውስጥ ትለወጣለች። ዛሬውኑ ይጀምሩ። አሁን ካሉበት ወንበር ተነስተው ለ5 ደቂቃ ፈጠን ብለው ይራመዱ። ሰውነትዎ ለዚህ ውሳኔዎ ነገ በታላቅ ጤና ያመሰግንዎታል።
በሰው ሰራሽ አስተውሎት የተሰራ ምስል
በአገራችን ኢትዮጵያ "ጤና ይስጥልኝ" ብለን ሰላምታ መለዋወጥ የተለመደ ቢሆንም፣ ዛሬ ግን ያ ጤና በቤታችን እና በቢሯችን ውስጥ በሚገኙ ምቹ ወንበሮች፣ በሞባይል ስልኮች እና በቴክኖሎጂ ምቾት እየተሰረቀ ይገኛል። በኢትዮጵያ የሕዝብ ጤና ኢንስቲትዩት (EPHI) ጥናቶች እንደሚያሳዩት፣ ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎች (እንደ የደም ግፊት፣ ስኳር እና የልብ በሽታ) በኢትዮጵያ ለሚከሰቱት ሞቶች ከ40% በላይ ድርሻ ይይዛሉ። ይህ አሀዝ በየዓመቱ በአሰቃቂ ሁኔታ እየጨመረ ነው።
የዝምታው ገዳይ ድምፅ
ብዙዎቻችን ቀኑን ሙሉ ተቀምጠን እንውላለን። በቢሮ ውስጥ ከኮምፒውተር ፊት፣ በትራንስፖርት መጨናነቅ ውስጥ በታክሲ ወንበር ላይ፣ ማታ ደግሞ ከቴሌቪዥን ፊት። ይህ "ተቀምጦ የመዋል" (Sedentary Lifestyle) አባዜ በኢትዮጵያውያን ዘንድ አዲስ እና አደገኛ ስጋት ሆኗል።
ጥናቶች እንደሚጠቁሙት በቀን ውስጥ ከ7-8 ሰዓታት በላይ መቀመጥ፣ ሰውነታችን "ተኝቻለሁ" ብሎ እንዲያስብ ያደርገዋል። በዚህ ጊዜ የደም ዝውውር ይገታል፣ ስኳርን የማቃጠል አቅማችን ይቀንሳል፣ ደም ስሮቻችንም መጥበብ ይጀምራሉ። ውጤቱም፦
የልብ ድካም፦ በድንገት የሚመጣና ቤተሰብን የሚበትን።
የስኳር በሽታ፦ ለዘላለም ከመድኃኒት ጋር የሚያቆራኝ።
የአእምሮ ጭንቀት፦ በብቸኝነት እና በድካም ስሜት የታጀበ።
የአምስት ደቂቃ ተዓምር (Brisk Walk)
ብዙዎቻችን የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ለማድረግ ውድ የጂም (Gym) ክፍያ ወይም ረጅም ሰዓት እንደሚያስፈልግ እናስባለን። ነገር ግን ሳይንሳዊ ጥናቶች የሚያረጋግጡት እውነት ሌላ ነው።
በየቀኑ ለ5 ደቂቃ ብቻ ፈጠን ያለ እርምጃ (Brisk Walk) መራመድ የሞት አደጋን በከፍተኛ ሁኔታ ይቀንሳል። ይህ እርምጃ ተራ እርምጃ ሳይሆን፣ ልብ ትርታዋ ትንሽ ከፍ የሚልበት፣ ነገር ግን ትንፋሽ የማይቆርጥ መሆን አለበት።
"አምስት ደቂቃ ለጤናማ ሰው አጭር ጊዜ ልትሆን ትችላለች፤ ለታመመ ሰው ግን አምስት ደቂቃ ሙሉ ሕይወቱ ናት።"
በኢትዮጵያዊ ሕይወት ውስጥ እንዴት እንተግብረው?
ይህንን ለውጥ ለማምጣት የግድ የአትሌት ትጥቅ አያስፈልግዎትም፦
ታክሲ ቀድመው ይውረዱ፦ መድረሻዎ ላይ ከመድረስዎ አንድ ፌርማታ ቀድመው በመውረድ ያቺን 5 ደቂቃ በፈጣን እርምጃ ይጓዙ።
ሊፍት ይተዉ፦ በህንፃዎች ላይ በሊፍት ፈንታ ደረጃን ይጠቀሙ።
የስልክ ወሬ በእግር፦ በስልክ ሲያወሩ ቁጭ ብለው ሳይሆን በቤትዎ ወይም በቢሮዎ ውስጥ በመመላለስ ይሁን።
የሻይ ሰዓት፦ በሻይ ዕረፍትዎ ወቅት ቁጭ ብለው ከማውራት፣ ሻይዎ እስኪመጣ ድረስ ለጥቂት ደቂቃዎች ወጣ ብለው ይንቀሳቀሱ።
አሳዛኙ እውነት እና ተስፋው
ዛሬ በኢትዮጵያ ሆስፒታሎች ውስጥ የምናያቸው ብዙዎቹ ወጣቶችና አዋቂዎች፣ "ኧረ በጊዜ በትንሹ በተንቀሳቀስኩ ኖሮ" ብለው የሚቆጩ ናቸው። የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ማጣት ጡንቻን ያደክማል፣ አጥንትን ያሳሳል፣ በመጨረሻም በሰው እጅ እንድንጠበቅ ያደርገናል።
ነገር ግን ተስፋ አለ! ያቺ ዛሬ የምትጀምሯት 5 ደቂቃ፣ ነገ ከልጆችዎ ጋር በደስታ የመጫወት ዕድልን ትሰጥዎታለች። ዛሬ የሚወሰድ አንድ እርምጃ፣ ነገ ሊመጣ ከሚችል የድንገተኛ ህመም እና የሕክምና ወጪ ይታደግዎታል።
ውድ አንባቢያን፦
ሕይወት በአምስት ደቂቃ ውስጥ ትለወጣለች። ዛሬውኑ ይጀምሩ። አሁን ካሉበት ወንበር ተነስተው ለ5 ደቂቃ ፈጠን ብለው ይራመዱ። ሰውነትዎ ለዚህ ውሳኔዎ ነገ በታላቅ ጤና ያመሰግንዎታል።
በሰው ሰራሽ አስተውሎት የተሰራ ምስል
6 months ago
የቢሮዎ ጠረጴዛ ከሽንት ቤት መቀመጫ ይበልጥ የቆሸሸ ሊሆን እንደሚችል ያውቃሉ? 🦠🚽
ብዙዎቻችን የቢሮ ጠረጴዛችንን እንደ ንጹህ ቦታ እናስባለን። ነገር ግን ሳይንሳዊ ጥናቶች እጅግ አስደንጋጭ ውጤት ይዘው መጥተዋል።
ጥናቱ ምን ይላል?
በአሪዞና ዩኒቨርሲቲ በማይክሮባዮሎጂ ፕሮፌሰሩ ዶ/ር ቻርልስ ጌርባ የተመራ ጥናት እንደሚያመለክተው፦
በአንድ ተራ የቢሮ ጠረጴዛ ላይ የሚገኘው የባክቴሪያ መጠን፣ በሽንት ቤት መቀመጫ (Toilet seat) ላይ ካለው በ 400 እጥፍ ይበልጣል! 😱
ቁጥሮቹ ሲነጻጸሩ፦
በቢሮ ጠረጴዛ ላይ፦ በአንድ ኢንች ስኩዌር በአማካይ 21,000 ባክቴሪያዎች ይገኛሉ።
በሽንት ቤት መቀመጫ ላይ፦ የሚገኘው ባክቴሪያ መጠን ከ 50 አይበልጥም።
ለምን እንዲህ ሆነ?
የጽዳት ልማድ፦ ሽንት ቤቶች በየቀኑ በፀረ-ባክቴሪያ ይጸዳሉ። የቢሮ ጠረጴዛዎች ግን ለሳምንታት ሳይጸዱ ሊቆዩ ይችላሉ።
ምግብ፦ ጠረጴዛ ላይ መመገብ ለባክቴሪያዎች መራቢያ የሚሆን ፍርፋሪ እና እርጥበት ይፈጥራል።
የቴክኖሎጂ ውጤቶች፦ ኪቦርድ፣ ማውስ እና ስልኮች የባክቴሪያ መደበቂያ ዋሻዎች ናቸው።
መፍትሄው፦
በየቀኑ የስራ ጠረጴዛዎን በንጽህና መጠበቂያ ማጽዳት እና እጅዎን አዘውትረው መታጠብ የጤናዎ ዋስትና ነው!
ብዙዎቻችን የቢሮ ጠረጴዛችንን እንደ ንጹህ ቦታ እናስባለን። ነገር ግን ሳይንሳዊ ጥናቶች እጅግ አስደንጋጭ ውጤት ይዘው መጥተዋል።
ጥናቱ ምን ይላል?
በአሪዞና ዩኒቨርሲቲ በማይክሮባዮሎጂ ፕሮፌሰሩ ዶ/ር ቻርልስ ጌርባ የተመራ ጥናት እንደሚያመለክተው፦
በአንድ ተራ የቢሮ ጠረጴዛ ላይ የሚገኘው የባክቴሪያ መጠን፣ በሽንት ቤት መቀመጫ (Toilet seat) ላይ ካለው በ 400 እጥፍ ይበልጣል! 😱
ቁጥሮቹ ሲነጻጸሩ፦
በቢሮ ጠረጴዛ ላይ፦ በአንድ ኢንች ስኩዌር በአማካይ 21,000 ባክቴሪያዎች ይገኛሉ።
በሽንት ቤት መቀመጫ ላይ፦ የሚገኘው ባክቴሪያ መጠን ከ 50 አይበልጥም።
ለምን እንዲህ ሆነ?
የጽዳት ልማድ፦ ሽንት ቤቶች በየቀኑ በፀረ-ባክቴሪያ ይጸዳሉ። የቢሮ ጠረጴዛዎች ግን ለሳምንታት ሳይጸዱ ሊቆዩ ይችላሉ።
ምግብ፦ ጠረጴዛ ላይ መመገብ ለባክቴሪያዎች መራቢያ የሚሆን ፍርፋሪ እና እርጥበት ይፈጥራል።
የቴክኖሎጂ ውጤቶች፦ ኪቦርድ፣ ማውስ እና ስልኮች የባክቴሪያ መደበቂያ ዋሻዎች ናቸው።
መፍትሄው፦
በየቀኑ የስራ ጠረጴዛዎን በንጽህና መጠበቂያ ማጽዳት እና እጅዎን አዘውትረው መታጠብ የጤናዎ ዋስትና ነው!
Sponsored by
Surafel
6 months ago
የሰው ልጅ መድኃኒቱ ሰው ነው፡ የጓደኝነትና የማህበራዊ ህይወት ፋይዳ በኢትዮጵያ አውድ
በሀገራችን ኢትዮጵያ ካሉን ድንቅ እሴቶች መካከል አንዱና ዋነኛው "ሰው ለሰው መድኃኒቱ ነው" የሚለው ብሂል ነው። ይህ አባባል በባህላችን ውስጥ ስር የሰደደ ቢሆንም፣ በዘመናዊው ሳይንስና በኒውሮ ሳይንቲስት ቤን ሬይን (Ben Rein) ጥናት ደግሞ አዲስና አስገራሚ ትርጉም አግኝቷል።
እንደ ሬይን ገለጻ፣ ጓደኝነትና ማህበራዊ ትስስር ለጤናችን ልክ እንደ ምግብ፣ እንቅልፍና ስፖርት እጅግ አስፈላጊ የሆኑ ምሰሶዎች ናቸው።
ማህበራዊ ግንኙነት እንደ አእምሮ ስፖርት
በኢትዮጵያ የቡና ስነስርዓት ላይ ተቀምጠን የምናወራው ጨዋታ፣ ወይም በጎረቤት የምናሳልፈው የ"እድር" እና የ"እቁብ" ጊዜያት ለደስታ ብቻ የሚደረጉ አይደሉም። እነዚህ ግንኙነቶች ለአእምሮአችን እንደ ከባድ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ (Brain Workout) ያገለግላሉ። ቤን ሬይን እንደሚለው፣ ከሰዎች ጋር በምናደርገው ንቁ ተሳትፎ አእምሮአችን "ኮግኒቲቭ ሪዘርቭ" (Cognitive Reserve) የተባለውን የመቋቋም አቅም ይገነባል።
ይህም በዕድሜ መግፋት የሚመጣውን የአእምሮ ዝገት (Dementia) የመከላከል አቅም አለው።
ከጓደኞች ጋር ጥቂት ደቂቃዎችን ማሳለፍ በአእምሮአችን ላይ የጠቆረውን ደመና ገፎ፣ ብርሃንና ጉልበት እንደሚሰጠን ሳይንሱ ያረጋግጣል። ይህ የሚሆነው በደስታ ጊዜ የሚመነጩ እንደ ኢንዶርፊን (Endorphins) ያሉ ኬሚካሎች በሰውነታችን ውስጥ ህመምን የመቋቋም አቅምን ስለሚጨምሩና ሥር የሰደደ መቆጣትን (Chronic Inflammation) ስለሚቀንሱ ነው።
የጤና ምሰሶ፡ ከልብ እስከ ስኳር ህመም
ብዙዎቻችን ለጤናችን ስንል የምንመገበውን ምግብ እንመርጣለን፣ ወይም እንቅስቃሴ እናደርጋለን። ነገር ግን "የማህበራዊ ህይወት አመጋገባችን" (Social Diet) ምን ይመስላል ብለን ጠይቀን አናውቅም። ጥናቶች እንደሚያሳዩት ጠንካራ ማህበራዊ ግንኙነት ያላቸው ሰዎች፦
👉ለልብ ድካምና ለስኳር ህመም የመጋለጥ እድላቸው አነስተኛ ነው።
👉ለጭንቀትና ለድብርት (Depression and Anxiety) የመሸነፍ አቅማቸው ዝቅተኛ ነው።
👉አስቸጋሪ ሁኔታዎችን የመቋቋም አቅማቸው (Resilience) የላቀ ነው።
👉በተቃራኒው፣ ብቸኝነትና ማህበራዊ መገለል እንደ ከባድ ጭንቀት (Chronic Stress) ይቆጠራሉ።
ዩኒቨርሲቲ ኦፍ ሂውስተን ውስጥ የተደረጉ ጥናቶች እንደሚያሳዩት፣ ማህበራዊ መገለል አእምሮ ከስትሮክ (Stroke) በኋላ ራሱን የመጠገን አቅሙን እንኳን ያዳክመዋል።
እንደ ተክል ውሃ ያስፈልገናል፡ የልዩነታችን ሚስጥር
ሁላችንም ማህበራዊ ግንኙነት ቢያስፈልገንም፣ የፍላጎታችን መጠን ግን ይለያያል። ቤን ሬይን ይህንን በዕፅዋት ምሳሌ ያስረዳዋል።
ተግባቢ (Extrovert) የሆኑ ሰዎች፦ ልክ እንደ ብዙ ውሃ እንደሚፈልግ ተክል ናቸው። በየቀኑ ከሰዎች ጋር መገናኘትና መጫወት ህይወት ይዘራባቸዋል።
ውስጠ-ታዋቂ (Introvert) የሆኑ ሰዎች፦ ደግሞ ልክ እንደ በረሃ ተክል (Cactus) ናቸው። አልፎ አልፎ የሚደረግ ግንኙነት ይበቃቸዋል፤ ውሃ ቢበዛባቸው ሊጠወልጉ ይችላሉ።
ይሁን እንጂ የትኛውም ተክል ያለ ውሃ ሊኖር እንደማይችል ሁሉ፣ "ብቸኝነት ይቀለኛል" የሚሉ ሰዎች እንኳ ቢያንስ አነስተኛውን የማህበራዊ ግንኙነት መጠን ማግኘት አለባቸው። ካልሆነ ግን አእምሮአቸው ግንኙነቶችን በጥቁር መነጽር ብቻ ማየት ይጀምርና ወደ ከፋ መገለል ይገፋቸዋል።
"የማህበራዊ አመጋገብ" ጥንቃቄ
ልክ ሆዳችንን የሚነፋን ወይም የሚያመን ምግብ እንደምንተወው ሁሉ፣ አእምሮአችንን የሚያቆስሉ ግንኙነቶችንም ማስወገድ ይገባናል። በኢትዮጵያ ማህበረሰብ ውስጥ "ዝምድና" እና "ጉርብትና" ትልቅ ቦታ ቢኖራቸውም፣ መርዛማ (Toxic) የሆኑ፣ ቁጣንና ጥላቻን የሚዘሩ ግንኙነቶች ለጤና ጠንቅ ናቸው። ሬይን እንደሚመክረው፣ ጤናማ ግንኙነት ማለት የመረዳዳት፣ የፍቅርና የጋራ ስሜት (Camaraderie) የሚሰጠን መሆን አለበት። ፌዝ፣ ማሸማቀቅና ጉልበተኝነት (Bullying) ለጤናችን የሚበጅ "ምግብ" አይደሉም።
ከጎጠኝነት ወደ ሰብአዊነት
በመጨረሻም፣ መጽሐፉ በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ (በተለይም በእኛ ሀገር አውድ) የሚታየውን የ"እኛ" እና "እነሱ" ክፍፍል በኒውሮ ሳይንስ እይታ ይተነትነዋል። የሰው ልጅ አእምሮ በጥንት ዘመን ራሱን ለመከላከል ሲል "የእኔ ወገን" የሚለውን የመለየት ተፈጥሮአዊ ዝንባሌ አለው። ነገር ግን አንድን ሰው "ከእኔ የተለየ ነው" ብለን ስናስብ፣ በአእምሮአችን ውስጥ ያለው የርህራሄ (Empathy) ማዕከል ስራውን ያቆማል።
ይህንን ተፈጥሮአዊ "ሃርድዌር" መቀየር ባንችልም፣ ግንዛቤ በመያዝ ግን ልንቆጣጠረው እንችላለን። ሌላውን ሰው እንደ ባዕድ ሳይሆን እንደ ራስ ወገን ማየት መቻል ለአእምሮአችን ሰላምና ለሰውነታችን ጤና ወሳኝ ነው።
ማጠቃለያ
በኢትዮጵያችን "ሰው የመድኃኒት ክምችት ነው" ቢባል ማጋነን አይሆንም። በሰፈር ጨዋታ፣ በቤተክርስቲያንና በመስጂድ ስነስርዓቶች፣ በስራ ቦታና በቡና ጠረጴዛ ዙሪያ የምናሳልፋቸው ጊዜያት የህይወታችንን ዘመን የሚቀጥሉ "ፋርማሲዎች" ናቸው። ስለሆነም ለጤናችን ስንል ጥሩ ጓደኞችን እንያዝ፣ መርዛማ ግንኙነቶችን እናስወግድ፣ እና ማህበራዊ ህይወታችንን እንደ ትልቅ የጤና መተግበሪያ እንመልከተው።
በሀገራችን ኢትዮጵያ ካሉን ድንቅ እሴቶች መካከል አንዱና ዋነኛው "ሰው ለሰው መድኃኒቱ ነው" የሚለው ብሂል ነው። ይህ አባባል በባህላችን ውስጥ ስር የሰደደ ቢሆንም፣ በዘመናዊው ሳይንስና በኒውሮ ሳይንቲስት ቤን ሬይን (Ben Rein) ጥናት ደግሞ አዲስና አስገራሚ ትርጉም አግኝቷል።
እንደ ሬይን ገለጻ፣ ጓደኝነትና ማህበራዊ ትስስር ለጤናችን ልክ እንደ ምግብ፣ እንቅልፍና ስፖርት እጅግ አስፈላጊ የሆኑ ምሰሶዎች ናቸው።
ማህበራዊ ግንኙነት እንደ አእምሮ ስፖርት
በኢትዮጵያ የቡና ስነስርዓት ላይ ተቀምጠን የምናወራው ጨዋታ፣ ወይም በጎረቤት የምናሳልፈው የ"እድር" እና የ"እቁብ" ጊዜያት ለደስታ ብቻ የሚደረጉ አይደሉም። እነዚህ ግንኙነቶች ለአእምሮአችን እንደ ከባድ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ (Brain Workout) ያገለግላሉ። ቤን ሬይን እንደሚለው፣ ከሰዎች ጋር በምናደርገው ንቁ ተሳትፎ አእምሮአችን "ኮግኒቲቭ ሪዘርቭ" (Cognitive Reserve) የተባለውን የመቋቋም አቅም ይገነባል።
ይህም በዕድሜ መግፋት የሚመጣውን የአእምሮ ዝገት (Dementia) የመከላከል አቅም አለው።
ከጓደኞች ጋር ጥቂት ደቂቃዎችን ማሳለፍ በአእምሮአችን ላይ የጠቆረውን ደመና ገፎ፣ ብርሃንና ጉልበት እንደሚሰጠን ሳይንሱ ያረጋግጣል። ይህ የሚሆነው በደስታ ጊዜ የሚመነጩ እንደ ኢንዶርፊን (Endorphins) ያሉ ኬሚካሎች በሰውነታችን ውስጥ ህመምን የመቋቋም አቅምን ስለሚጨምሩና ሥር የሰደደ መቆጣትን (Chronic Inflammation) ስለሚቀንሱ ነው።
የጤና ምሰሶ፡ ከልብ እስከ ስኳር ህመም
ብዙዎቻችን ለጤናችን ስንል የምንመገበውን ምግብ እንመርጣለን፣ ወይም እንቅስቃሴ እናደርጋለን። ነገር ግን "የማህበራዊ ህይወት አመጋገባችን" (Social Diet) ምን ይመስላል ብለን ጠይቀን አናውቅም። ጥናቶች እንደሚያሳዩት ጠንካራ ማህበራዊ ግንኙነት ያላቸው ሰዎች፦
👉ለልብ ድካምና ለስኳር ህመም የመጋለጥ እድላቸው አነስተኛ ነው።
👉ለጭንቀትና ለድብርት (Depression and Anxiety) የመሸነፍ አቅማቸው ዝቅተኛ ነው።
👉አስቸጋሪ ሁኔታዎችን የመቋቋም አቅማቸው (Resilience) የላቀ ነው።
👉በተቃራኒው፣ ብቸኝነትና ማህበራዊ መገለል እንደ ከባድ ጭንቀት (Chronic Stress) ይቆጠራሉ።
ዩኒቨርሲቲ ኦፍ ሂውስተን ውስጥ የተደረጉ ጥናቶች እንደሚያሳዩት፣ ማህበራዊ መገለል አእምሮ ከስትሮክ (Stroke) በኋላ ራሱን የመጠገን አቅሙን እንኳን ያዳክመዋል።
እንደ ተክል ውሃ ያስፈልገናል፡ የልዩነታችን ሚስጥር
ሁላችንም ማህበራዊ ግንኙነት ቢያስፈልገንም፣ የፍላጎታችን መጠን ግን ይለያያል። ቤን ሬይን ይህንን በዕፅዋት ምሳሌ ያስረዳዋል።
ተግባቢ (Extrovert) የሆኑ ሰዎች፦ ልክ እንደ ብዙ ውሃ እንደሚፈልግ ተክል ናቸው። በየቀኑ ከሰዎች ጋር መገናኘትና መጫወት ህይወት ይዘራባቸዋል።
ውስጠ-ታዋቂ (Introvert) የሆኑ ሰዎች፦ ደግሞ ልክ እንደ በረሃ ተክል (Cactus) ናቸው። አልፎ አልፎ የሚደረግ ግንኙነት ይበቃቸዋል፤ ውሃ ቢበዛባቸው ሊጠወልጉ ይችላሉ።
ይሁን እንጂ የትኛውም ተክል ያለ ውሃ ሊኖር እንደማይችል ሁሉ፣ "ብቸኝነት ይቀለኛል" የሚሉ ሰዎች እንኳ ቢያንስ አነስተኛውን የማህበራዊ ግንኙነት መጠን ማግኘት አለባቸው። ካልሆነ ግን አእምሮአቸው ግንኙነቶችን በጥቁር መነጽር ብቻ ማየት ይጀምርና ወደ ከፋ መገለል ይገፋቸዋል።
"የማህበራዊ አመጋገብ" ጥንቃቄ
ልክ ሆዳችንን የሚነፋን ወይም የሚያመን ምግብ እንደምንተወው ሁሉ፣ አእምሮአችንን የሚያቆስሉ ግንኙነቶችንም ማስወገድ ይገባናል። በኢትዮጵያ ማህበረሰብ ውስጥ "ዝምድና" እና "ጉርብትና" ትልቅ ቦታ ቢኖራቸውም፣ መርዛማ (Toxic) የሆኑ፣ ቁጣንና ጥላቻን የሚዘሩ ግንኙነቶች ለጤና ጠንቅ ናቸው። ሬይን እንደሚመክረው፣ ጤናማ ግንኙነት ማለት የመረዳዳት፣ የፍቅርና የጋራ ስሜት (Camaraderie) የሚሰጠን መሆን አለበት። ፌዝ፣ ማሸማቀቅና ጉልበተኝነት (Bullying) ለጤናችን የሚበጅ "ምግብ" አይደሉም።
ከጎጠኝነት ወደ ሰብአዊነት
በመጨረሻም፣ መጽሐፉ በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ (በተለይም በእኛ ሀገር አውድ) የሚታየውን የ"እኛ" እና "እነሱ" ክፍፍል በኒውሮ ሳይንስ እይታ ይተነትነዋል። የሰው ልጅ አእምሮ በጥንት ዘመን ራሱን ለመከላከል ሲል "የእኔ ወገን" የሚለውን የመለየት ተፈጥሮአዊ ዝንባሌ አለው። ነገር ግን አንድን ሰው "ከእኔ የተለየ ነው" ብለን ስናስብ፣ በአእምሮአችን ውስጥ ያለው የርህራሄ (Empathy) ማዕከል ስራውን ያቆማል።
ይህንን ተፈጥሮአዊ "ሃርድዌር" መቀየር ባንችልም፣ ግንዛቤ በመያዝ ግን ልንቆጣጠረው እንችላለን። ሌላውን ሰው እንደ ባዕድ ሳይሆን እንደ ራስ ወገን ማየት መቻል ለአእምሮአችን ሰላምና ለሰውነታችን ጤና ወሳኝ ነው።
ማጠቃለያ
በኢትዮጵያችን "ሰው የመድኃኒት ክምችት ነው" ቢባል ማጋነን አይሆንም። በሰፈር ጨዋታ፣ በቤተክርስቲያንና በመስጂድ ስነስርዓቶች፣ በስራ ቦታና በቡና ጠረጴዛ ዙሪያ የምናሳልፋቸው ጊዜያት የህይወታችንን ዘመን የሚቀጥሉ "ፋርማሲዎች" ናቸው። ስለሆነም ለጤናችን ስንል ጥሩ ጓደኞችን እንያዝ፣ መርዛማ ግንኙነቶችን እናስወግድ፣ እና ማህበራዊ ህይወታችንን እንደ ትልቅ የጤና መተግበሪያ እንመልከተው።
6 months ago
🚀 ግቦችዎና ምኞቶችዎ እንዳይሳኩ ያደረጉ 7 ምክንያቶች!
ብዙዎቻችን ጠንክረን እንሰራለን፣ ነገር ግን የፈለግነውን ውጤት ሳናገኝ እንቀራለን። ለዚህ ደግሞ ዋና ዋናዎቹ እንቅፋቶች የሚከተሉት ናቸው፦
1️⃣ ግልጽ ያልሆኑ (ደብዛዛ) ግቦች መቅረጽ፦ ግብዎ በግልጽ ካልታወቀ የት እንደሚደርሱ አያውቁም። "ሀብታም መሆን እፈልጋለሁ" ከማለት ይልቅ "በዚህ አመት ይህን ያህል ብር አተርፋለሁ" የሚል ግልጽ ግብ ይኑርዎት።
2️⃣ የስኬት ስትራቴጂ አለመኖር፦ ያለ እቅድና ስልት የሚደረግ ጉዞ መድረሻ የለውም። ግብዎን ለመምታት ዝርዝር የድርጊት መርሃ ግብር ያስፈልግዎታል።
3️⃣ እድገትን አለመከታተል፦ የት እንደደረሱና ምን እንደቀረዎት ካልገመገሙ ስህተትዎን ለማረም እድል አያገኙም።
4️⃣ አላስፈላጊ አካባቢና ጓደኝነት፦ በዙሪያዎ ያሉ ሰዎች ወይም ያለንበት ሁኔታ ለለውጥ የማይረዱ ከሆኑ ወደ ኋላ ይጎትቱዎታል። እድገትዎን የሚደግፍ አካባቢ ይፍጠሩ።
5️⃣ አዲስ አሰራርን አለመከተል፦ ሁልጊዜ በሚያደርጉት መንገድ አዲስ ውጤት መጠበቅ አይቻልም። አዳዲስ ዘዴዎችንና አቀራረቦችን ይሞክሩ።
6️⃣ የሰዎችን እርዳታ ብቻ መጠበቅ፦ ስኬት የእርስዎ ሃላፊነት ነው። ከሌሎች እርዳታ ከመጠበቅ ይልቅ በራስዎ ጥረት ላይ ያተኩሩ።
7️⃣ በቶሎ ተስፋ መቁረጥ፦ ብዙዎች ስኬት ደጃፍ ላይ ሲደርሱ ፊታቸውን ያዞራሉ። ጽናት የሁሉም ስኬታማ ሰዎች የጋራ መገለጫ ነው።
💡 አስታውሱ፦ ስኬት በአንድ ጀምበር የሚመጣ ሳይሆን በእነዚህ ነጥቦች ላይ በመስራት የሚገኝ ውጤት ነው!
ብዙዎቻችን ጠንክረን እንሰራለን፣ ነገር ግን የፈለግነውን ውጤት ሳናገኝ እንቀራለን። ለዚህ ደግሞ ዋና ዋናዎቹ እንቅፋቶች የሚከተሉት ናቸው፦
1️⃣ ግልጽ ያልሆኑ (ደብዛዛ) ግቦች መቅረጽ፦ ግብዎ በግልጽ ካልታወቀ የት እንደሚደርሱ አያውቁም። "ሀብታም መሆን እፈልጋለሁ" ከማለት ይልቅ "በዚህ አመት ይህን ያህል ብር አተርፋለሁ" የሚል ግልጽ ግብ ይኑርዎት።
2️⃣ የስኬት ስትራቴጂ አለመኖር፦ ያለ እቅድና ስልት የሚደረግ ጉዞ መድረሻ የለውም። ግብዎን ለመምታት ዝርዝር የድርጊት መርሃ ግብር ያስፈልግዎታል።
3️⃣ እድገትን አለመከታተል፦ የት እንደደረሱና ምን እንደቀረዎት ካልገመገሙ ስህተትዎን ለማረም እድል አያገኙም።
4️⃣ አላስፈላጊ አካባቢና ጓደኝነት፦ በዙሪያዎ ያሉ ሰዎች ወይም ያለንበት ሁኔታ ለለውጥ የማይረዱ ከሆኑ ወደ ኋላ ይጎትቱዎታል። እድገትዎን የሚደግፍ አካባቢ ይፍጠሩ።
5️⃣ አዲስ አሰራርን አለመከተል፦ ሁልጊዜ በሚያደርጉት መንገድ አዲስ ውጤት መጠበቅ አይቻልም። አዳዲስ ዘዴዎችንና አቀራረቦችን ይሞክሩ።
6️⃣ የሰዎችን እርዳታ ብቻ መጠበቅ፦ ስኬት የእርስዎ ሃላፊነት ነው። ከሌሎች እርዳታ ከመጠበቅ ይልቅ በራስዎ ጥረት ላይ ያተኩሩ።
7️⃣ በቶሎ ተስፋ መቁረጥ፦ ብዙዎች ስኬት ደጃፍ ላይ ሲደርሱ ፊታቸውን ያዞራሉ። ጽናት የሁሉም ስኬታማ ሰዎች የጋራ መገለጫ ነው።
💡 አስታውሱ፦ ስኬት በአንድ ጀምበር የሚመጣ ሳይሆን በእነዚህ ነጥቦች ላይ በመስራት የሚገኝ ውጤት ነው!
6 months ago
ራስን መቆጣጠር ለምን ይከሽፋል? የልማድ ሳይንስ ሚስጥር
ብዙዎቻችን አዲስ አመት ሲመጣ ወይም አዲስ ውሳኔ ስናስተላልፍ የምንታመነው በ"ቆራጥነት" ወይም በ"ፍላጎት ኃይል" (Willpower) ላይ ነው። ሆኖም ግን፣ የደቡብ ካሊፎርኒያ ዩኒቨርሲቲ ፕሮፌሰር የሆኑት ዌንዲ ዉድ እንደሚሉት፣ "ራስን መቆጣጠር ወይም ዲሲፕሊን ከመጠን በላይ ግምት ተሰጥቶታል።" እውነተኛ ለውጥ የሚመጣው በውስጣዊ ጥንካሬ ሳይሆን በዙሪያችን ባለው ሁኔታ (Environment) ላይ በሚደረግ ማሻሻያ ነው።
1. መሰናክሎችን የመፍጠር ጥበብ
መጥፎ ልማድን ለማቆም ምርጡ መንገድ በድርጊቱ እና በእርስዎ መካከል መሰናክል (Friction) መፍጠር ነው። ዌንዲ ዉድ እንደሚሉት፣ "አንድን ነገር ለማድረግ ብዙ ጥረት በጠየቀን ቁጥር፣ ያንን ነገር የማድረግ እድላችን ይቀንሳል።"
ምሳሌ፦ ስልክዎን ደጋግመው የመመልከት ልማድ ካለብዎት፣ ስልኩን ፊት ለፊቱ እንዲደፋ አድርገው ጠረጴዛ ላይ ያስቀምጡት። ይህ መጠነኛ መሰናክል ትኩረትዎ እንዳይከፋፍል ይረዳል።
የአመጋገብ ልማድ፦ ጤናማ ያልሆኑ ምግቦችን ከመመገብ ለመቆጠብ፣ እነዚያን ምግቦች በቀላሉ በማይደረስበት ቦታ ወይም ጓዳ ውስጥ ደብቀው ያስቀምጡ።
2. እንቅፋቶችን ማስወገድ
ጥሩ ልማድ እንዲኖረን ደግሞ በድርጊቱ ዙሪያ ያሉትን እንቅፋቶች በሙሉ ማጽዳት አለብን። ዌንዲ ዉድ እራሷ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ለማድረግ የምትጠቀመውን ዘዴ እንዲህ ትገልጻለች፦ "ጠዋት ተነስቼ ልብስ የመቀየር ስንፍና እንዳያሸንፈኝ፣ ማታ ስተኛ የስፖርት ልብሴን ለብሼ እተኛለሁ።"
ይህ "ቀድሞ የመዘጋጀት" ስልት አእምሮ ጠዋት ላይ ውሳኔ እንዳያበዛ ያደርገዋል። ሌላው ትልቅ እንቅፋት ርቀት ነው። በአንድ ጥናት መሰረት፣ ከቤታቸው 6 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ጂም ያላቸው ሰዎች በወር በአማካይ 5 ጊዜ ሲሄዱ፣ ርቀቱ ወደ 8 ኪሎ ሜትር ሲያድግ ግን በወር አንዴ ብቻ መሄድ ይጀምራሉ። ያቺ የ2 ኪሎ ሜትር ልዩነት ብቻ ፍላጎትን ልታጠፋ ትችላለች።
3. የሁለት ወራት ህግ እና አውቶማቲክ አእምሮ
አንድ ተግባር "ልማድ" ሆኗል የሚባለው ያለምንም ማቅማማት እና ትግል ስናከናውነው ነው። ሳይንሳዊ ጥናቶች እንደሚያሳዩት፣ አንድ አዲስ ነገር ወደ ልማድ ለመቀየር በአማካይ ሁለት ወራት አካባቢ ይፈጃል።
በዚህ ጊዜ ውስጥ ድርጊቱ ከአእምሯችን "ንቁ የውሳኔ ሰጪ ክፍል" ወደ "አውቶማቲክ ክፍል" ይሸጋገራል። እኛ በየቀኑ የምናከናውናቸው ተግባራት 43% የሚሆኑት አውቶማቲክ ናቸው። ለምሳሌ፦
ጥርስ መቦረሽ
መኪና መንዳት
ወደ ስራ ሲሄዱ የሚከተሉት መንገድ
ስኬታማ የሆኑ ሰዎች ከአማካይ ሰው የሚለዩት በከፍተኛ ቆራጥነት ሳይሆን፣ ግባቸውን የሚደግፉ አውቶማቲክ ልማዶችን መገንባት በመቻላቸው ነው።
ከቤት የመስራት ፈተና እና የዲሲፕሊን መላላት
ብዙ ጎበዝ ሰራተኞች ከቤት ሲሰሩ ውጤታማነታቸው ይቀንሳል። ለዚህ ምክንያቱ የቢሮው "መዋቅር" (Structure) መጥፋት ነው። ቢሮ ስንሄድ የምንከተለው ወጥ መንገድ፣ የምንቀመጥበት ቦታ እና በዙሪያችን ያሉ ሰዎች በራሳቸው ስራ ላይ እንድናተኩር የሚገፋፉ "ምልክቶች" (Cues) ናቸው።
ቤት ውስጥ ግን እነዚህ ምልክቶች የሉም። በምትኩ ትኩረትን የሚሰርቁ እንደ ቴሌቪዥን፣ አልጋ ወይም ማቀዝቀዣ ያሉ "መሰናክሎች" ይበዛሉ። ስለዚህ ስኬታማ ለመሆን ቤትዎ ውስጥ የራስዎን የስራ መዋቅር እና ምልክቶች መፍጠር ግድ ይላል።
"የራስን ፍላጎት የመካድ ተቃራኒ ውጤት" (Ironic Effect of Self-Denial)
ዌንዲ ዉድ አንድ አስገራሚ እውነታ ታነሳለች፦ አንድን ነገር "አላደርግም" ብለው በጨከኑ ቁጥር፣ ያ ነገር የበለጠ ያምርዎታል።
"አንድን ነገር ላለማድረግ በጣርክ ቁጥር፣ የማድረግ ፍላጎትህ ይጨምራል።"
ይህ በምግብ አመጋገብ (Diet) ላይ በግልጽ ይታያል። ምግብን በከፍተኛ ሁኔታ ለሚከለክሉ ሰዎች አእምሯቸው ስለ ምግብ ብቻ ማሰብ ይጀምራል። እንቅልፍ ለመተኛት በጨከንን ቁጥር እንቅልፍ እንደሚርቀን ሁሉ ማለት ነው። ስለዚህ መፍትሄው "አላደርግም" ብሎ መታገል ሳይሆን፣ ድርጊቱን የሚያስነሳውን አጋጣሚ (Trigger) መቀየር ነው።
ጤናማ እርጅና እና የረጅም ጊዜ ስኬት
ልማዶቻችን ዛሬ የምንሰራቸው ስራዎች ብቻ ሳይሆኑ፣ ለወደፊት ጤናችንም መሰረት ናቸው። የዙሪክ ዩኒቨርሲቲ "Healthy Longevity Center" እንደሚጠቁመው፣ ጤናማ ህይወት የሚጀምረው በአስተሳሰብ ለውጥ ነው።
ለተሻለ ለውጥ 4 ዋና ዋና ነጥቦች፦
ቀላል አድርገው፦ አዲሱን ልማድ ለመጀመር የሚያስፈልገውን ጥረት በትንሹ ይቀንሱ።
ደስታን ይጨምሩበት፦ ዌንዲ ዉድ አሰልቺውን ስፖርት በምትሰራበት ጊዜ የምትወደውን ልብ ወለድ ታነባለች። እርስዎም የሚወዱትን ነገር ከሚከብድዎት ስራ ጋር ያጣምሩት።
ወጥነት ይኑርዎት፦ ለሁለት ወራት ያህል ሳይቆራረጡ ያድርጉት።
አካባቢዎን ይቀይሩ፦ ፈተናዎችን ከዓይን ያርቁ፣ አጋዥ ነገሮችን ፊት ለፊት ያስቀምጡ።
ማጠቃለያ
ልማድ መቀየር የፍላጎት ጥንካሬ ጉዳይ ብቻ አይደለም፤ የንድፍ (Design) ጉዳይ እንጂ። ህይወትዎን ለመቀየር ከፈለጉ ባህሪዎን ለመቆጣጠር ከመታገል ይልቅ፣ ባህሪዎን የሚወስነውን አካባቢዎን በሳይንሳዊ መንገድ ያዋቅሩ።
ብዙዎቻችን አዲስ አመት ሲመጣ ወይም አዲስ ውሳኔ ስናስተላልፍ የምንታመነው በ"ቆራጥነት" ወይም በ"ፍላጎት ኃይል" (Willpower) ላይ ነው። ሆኖም ግን፣ የደቡብ ካሊፎርኒያ ዩኒቨርሲቲ ፕሮፌሰር የሆኑት ዌንዲ ዉድ እንደሚሉት፣ "ራስን መቆጣጠር ወይም ዲሲፕሊን ከመጠን በላይ ግምት ተሰጥቶታል።" እውነተኛ ለውጥ የሚመጣው በውስጣዊ ጥንካሬ ሳይሆን በዙሪያችን ባለው ሁኔታ (Environment) ላይ በሚደረግ ማሻሻያ ነው።
1. መሰናክሎችን የመፍጠር ጥበብ
መጥፎ ልማድን ለማቆም ምርጡ መንገድ በድርጊቱ እና በእርስዎ መካከል መሰናክል (Friction) መፍጠር ነው። ዌንዲ ዉድ እንደሚሉት፣ "አንድን ነገር ለማድረግ ብዙ ጥረት በጠየቀን ቁጥር፣ ያንን ነገር የማድረግ እድላችን ይቀንሳል።"
ምሳሌ፦ ስልክዎን ደጋግመው የመመልከት ልማድ ካለብዎት፣ ስልኩን ፊት ለፊቱ እንዲደፋ አድርገው ጠረጴዛ ላይ ያስቀምጡት። ይህ መጠነኛ መሰናክል ትኩረትዎ እንዳይከፋፍል ይረዳል።
የአመጋገብ ልማድ፦ ጤናማ ያልሆኑ ምግቦችን ከመመገብ ለመቆጠብ፣ እነዚያን ምግቦች በቀላሉ በማይደረስበት ቦታ ወይም ጓዳ ውስጥ ደብቀው ያስቀምጡ።
2. እንቅፋቶችን ማስወገድ
ጥሩ ልማድ እንዲኖረን ደግሞ በድርጊቱ ዙሪያ ያሉትን እንቅፋቶች በሙሉ ማጽዳት አለብን። ዌንዲ ዉድ እራሷ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ለማድረግ የምትጠቀመውን ዘዴ እንዲህ ትገልጻለች፦ "ጠዋት ተነስቼ ልብስ የመቀየር ስንፍና እንዳያሸንፈኝ፣ ማታ ስተኛ የስፖርት ልብሴን ለብሼ እተኛለሁ።"
ይህ "ቀድሞ የመዘጋጀት" ስልት አእምሮ ጠዋት ላይ ውሳኔ እንዳያበዛ ያደርገዋል። ሌላው ትልቅ እንቅፋት ርቀት ነው። በአንድ ጥናት መሰረት፣ ከቤታቸው 6 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ጂም ያላቸው ሰዎች በወር በአማካይ 5 ጊዜ ሲሄዱ፣ ርቀቱ ወደ 8 ኪሎ ሜትር ሲያድግ ግን በወር አንዴ ብቻ መሄድ ይጀምራሉ። ያቺ የ2 ኪሎ ሜትር ልዩነት ብቻ ፍላጎትን ልታጠፋ ትችላለች።
3. የሁለት ወራት ህግ እና አውቶማቲክ አእምሮ
አንድ ተግባር "ልማድ" ሆኗል የሚባለው ያለምንም ማቅማማት እና ትግል ስናከናውነው ነው። ሳይንሳዊ ጥናቶች እንደሚያሳዩት፣ አንድ አዲስ ነገር ወደ ልማድ ለመቀየር በአማካይ ሁለት ወራት አካባቢ ይፈጃል።
በዚህ ጊዜ ውስጥ ድርጊቱ ከአእምሯችን "ንቁ የውሳኔ ሰጪ ክፍል" ወደ "አውቶማቲክ ክፍል" ይሸጋገራል። እኛ በየቀኑ የምናከናውናቸው ተግባራት 43% የሚሆኑት አውቶማቲክ ናቸው። ለምሳሌ፦
ጥርስ መቦረሽ
መኪና መንዳት
ወደ ስራ ሲሄዱ የሚከተሉት መንገድ
ስኬታማ የሆኑ ሰዎች ከአማካይ ሰው የሚለዩት በከፍተኛ ቆራጥነት ሳይሆን፣ ግባቸውን የሚደግፉ አውቶማቲክ ልማዶችን መገንባት በመቻላቸው ነው።
ከቤት የመስራት ፈተና እና የዲሲፕሊን መላላት
ብዙ ጎበዝ ሰራተኞች ከቤት ሲሰሩ ውጤታማነታቸው ይቀንሳል። ለዚህ ምክንያቱ የቢሮው "መዋቅር" (Structure) መጥፋት ነው። ቢሮ ስንሄድ የምንከተለው ወጥ መንገድ፣ የምንቀመጥበት ቦታ እና በዙሪያችን ያሉ ሰዎች በራሳቸው ስራ ላይ እንድናተኩር የሚገፋፉ "ምልክቶች" (Cues) ናቸው።
ቤት ውስጥ ግን እነዚህ ምልክቶች የሉም። በምትኩ ትኩረትን የሚሰርቁ እንደ ቴሌቪዥን፣ አልጋ ወይም ማቀዝቀዣ ያሉ "መሰናክሎች" ይበዛሉ። ስለዚህ ስኬታማ ለመሆን ቤትዎ ውስጥ የራስዎን የስራ መዋቅር እና ምልክቶች መፍጠር ግድ ይላል።
"የራስን ፍላጎት የመካድ ተቃራኒ ውጤት" (Ironic Effect of Self-Denial)
ዌንዲ ዉድ አንድ አስገራሚ እውነታ ታነሳለች፦ አንድን ነገር "አላደርግም" ብለው በጨከኑ ቁጥር፣ ያ ነገር የበለጠ ያምርዎታል።
"አንድን ነገር ላለማድረግ በጣርክ ቁጥር፣ የማድረግ ፍላጎትህ ይጨምራል።"
ይህ በምግብ አመጋገብ (Diet) ላይ በግልጽ ይታያል። ምግብን በከፍተኛ ሁኔታ ለሚከለክሉ ሰዎች አእምሯቸው ስለ ምግብ ብቻ ማሰብ ይጀምራል። እንቅልፍ ለመተኛት በጨከንን ቁጥር እንቅልፍ እንደሚርቀን ሁሉ ማለት ነው። ስለዚህ መፍትሄው "አላደርግም" ብሎ መታገል ሳይሆን፣ ድርጊቱን የሚያስነሳውን አጋጣሚ (Trigger) መቀየር ነው።
ጤናማ እርጅና እና የረጅም ጊዜ ስኬት
ልማዶቻችን ዛሬ የምንሰራቸው ስራዎች ብቻ ሳይሆኑ፣ ለወደፊት ጤናችንም መሰረት ናቸው። የዙሪክ ዩኒቨርሲቲ "Healthy Longevity Center" እንደሚጠቁመው፣ ጤናማ ህይወት የሚጀምረው በአስተሳሰብ ለውጥ ነው።
ለተሻለ ለውጥ 4 ዋና ዋና ነጥቦች፦
ቀላል አድርገው፦ አዲሱን ልማድ ለመጀመር የሚያስፈልገውን ጥረት በትንሹ ይቀንሱ።
ደስታን ይጨምሩበት፦ ዌንዲ ዉድ አሰልቺውን ስፖርት በምትሰራበት ጊዜ የምትወደውን ልብ ወለድ ታነባለች። እርስዎም የሚወዱትን ነገር ከሚከብድዎት ስራ ጋር ያጣምሩት።
ወጥነት ይኑርዎት፦ ለሁለት ወራት ያህል ሳይቆራረጡ ያድርጉት።
አካባቢዎን ይቀይሩ፦ ፈተናዎችን ከዓይን ያርቁ፣ አጋዥ ነገሮችን ፊት ለፊት ያስቀምጡ።
ማጠቃለያ
ልማድ መቀየር የፍላጎት ጥንካሬ ጉዳይ ብቻ አይደለም፤ የንድፍ (Design) ጉዳይ እንጂ። ህይወትዎን ለመቀየር ከፈለጉ ባህሪዎን ለመቆጣጠር ከመታገል ይልቅ፣ ባህሪዎን የሚወስነውን አካባቢዎን በሳይንሳዊ መንገድ ያዋቅሩ።
6 months ago
የፍቅር ግንኙነታችሁን ለማሻሻል ይቺን አንዲት ጥያቄ ብቻ ጠይቁ!
ብዙዎቻችን አጋራችንን በሚገባ የምናውቀው ይመስለናል፤ ነገር ግን ትክክለኛ ፍላጎታቸውን ሳንረዳ ቀርተን ለግጭት እና ለቅሬታ የምንጋለጥበት ጊዜ ቀላል አይደለም።
የሃርቫርድ ዩኒቨርሲቲ የስነ-ልቦና ፕሮፌሰር የሆኑት አሽቪኒ ናድካርኒ እንደሚሉት ከሆነ፣ ማንኛውንም የፍቅር ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ ለመውሰድ የምትረዳ አንዲት ቀላል ጥያቄ አለች፦
"የተወደድክ/ሽ እንደሆነ እንዲሰማህ/ሽ የሚያደርግህ/ሽ ምንድን ነው?"
ለምን መጠየቅ አስፈለገ?
የፍቅር ቋንቋን ለመለየት፦ አንዳንዶች በስጦታ፣ አንዳንዶች አብሮ በመሆን፣ ሌሎቹ ደግሞ በምስጋና ሊደሰቱ ይችላሉ። ጥያቄው አጋራችሁ ፍቅርን የሚረዳበትን መንገድ (Love Language) በግልጽ እንድታውቁ ይረዳል።
ግምትን ያስቀራል፦ "ይሄን ብሰራት ደስ ይላታል" ብሎ ከመገመት ይልቅ፣ የልብ ፍላጎቷን አውቆ ማቅረብ እርካታን ይጨምራል።
ግንኙነትን ያድሳል፦ የሰው ልጅ ፍላጎት በጊዜ ሂደት ስለሚቀያየር፣ ይህን ጥያቄ አልፎ አልፎ መጠየቅ ግንኙነቱ ሁሌም አዲስ እንዲሆን ያደርጋል።
ባለሙያዋ ምን ይላሉ?
"ይህ ጥያቄ ከ5 ዓመት የፍቅር ቆይታ በላይ ጥንዶችን ሊያቀራርብ ይችላል። እርስ በእርስ መደማመጥና መረዳት ግንኙነቱ ጠንካራና አስተማማኝ እንዲሆን መሰረት ይጥላል።"
ብዙዎቻችን አጋራችንን በሚገባ የምናውቀው ይመስለናል፤ ነገር ግን ትክክለኛ ፍላጎታቸውን ሳንረዳ ቀርተን ለግጭት እና ለቅሬታ የምንጋለጥበት ጊዜ ቀላል አይደለም።
የሃርቫርድ ዩኒቨርሲቲ የስነ-ልቦና ፕሮፌሰር የሆኑት አሽቪኒ ናድካርኒ እንደሚሉት ከሆነ፣ ማንኛውንም የፍቅር ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ ለመውሰድ የምትረዳ አንዲት ቀላል ጥያቄ አለች፦
"የተወደድክ/ሽ እንደሆነ እንዲሰማህ/ሽ የሚያደርግህ/ሽ ምንድን ነው?"
ለምን መጠየቅ አስፈለገ?
የፍቅር ቋንቋን ለመለየት፦ አንዳንዶች በስጦታ፣ አንዳንዶች አብሮ በመሆን፣ ሌሎቹ ደግሞ በምስጋና ሊደሰቱ ይችላሉ። ጥያቄው አጋራችሁ ፍቅርን የሚረዳበትን መንገድ (Love Language) በግልጽ እንድታውቁ ይረዳል።
ግምትን ያስቀራል፦ "ይሄን ብሰራት ደስ ይላታል" ብሎ ከመገመት ይልቅ፣ የልብ ፍላጎቷን አውቆ ማቅረብ እርካታን ይጨምራል።
ግንኙነትን ያድሳል፦ የሰው ልጅ ፍላጎት በጊዜ ሂደት ስለሚቀያየር፣ ይህን ጥያቄ አልፎ አልፎ መጠየቅ ግንኙነቱ ሁሌም አዲስ እንዲሆን ያደርጋል።
ባለሙያዋ ምን ይላሉ?
"ይህ ጥያቄ ከ5 ዓመት የፍቅር ቆይታ በላይ ጥንዶችን ሊያቀራርብ ይችላል። እርስ በእርስ መደማመጥና መረዳት ግንኙነቱ ጠንካራና አስተማማኝ እንዲሆን መሰረት ይጥላል።"
Sponsored by
Surafel
6 months ago
በጣም የቆዩ (የጠቆሩ) ሙዞችን ለልጆች ከመስጠት ይቆጠቡ!
ብዙዎቻችን ሙዝ በበሰለ ቁጥር ይጣፍጣል ብለን እናስባለን፤ ነገር ግን ከመጠን በላይ የበሰሉ እና የጠቆሩ ሙዞች ለልጆች ጤና ተስማሚ ላይሆኑ እንደሚችሉ ያውቃሉ?
ምክንያቱም፦
በሙዝ ውስጥ የሚገኘው የተፈጥሮ ስኳር እየቆየ ሲሄድ Natural Fermentation (ተፈጥሯዊ መብላላት) ይካሄዳል። በዚህም ምክንያት፦
ጥሬ (አረንጓዴ) ሙዝ፡ ምንም ዓይነት አልኮል የለውም።
መካከለኛ የበሰለ ሙዝ፡ በጣም ጥቂት ወይም ምንም የሚባል አልኮል የለውም።
የጠቆረ (Overripe) ሙዝ፡ በተፈጥሯዊ መብላላት ምክንያት በውስጡ መጠነኛ አልኮል ይፈጠራል።
ልብ ሊባል የሚገባው፦
ይህ አልኮል ሙዙ ሲበስል ወይም በሙቀት ሲገነፍል ይበናል (Evaporate ያደርጋል)። ስለዚህ እነዚህን ሙዞች ለጥሬ አመጋገብ ከመጠቀም ይልቅ ለኬክ፣ ለዳቦ ወይም ለተለያዩ የዱቄት ምግቦች ማጣፈጫነት ቢጠቀሙባቸው ይመረጣል።
seledadotio
seledadotio
ብዙዎቻችን ሙዝ በበሰለ ቁጥር ይጣፍጣል ብለን እናስባለን፤ ነገር ግን ከመጠን በላይ የበሰሉ እና የጠቆሩ ሙዞች ለልጆች ጤና ተስማሚ ላይሆኑ እንደሚችሉ ያውቃሉ?
ምክንያቱም፦
በሙዝ ውስጥ የሚገኘው የተፈጥሮ ስኳር እየቆየ ሲሄድ Natural Fermentation (ተፈጥሯዊ መብላላት) ይካሄዳል። በዚህም ምክንያት፦
ጥሬ (አረንጓዴ) ሙዝ፡ ምንም ዓይነት አልኮል የለውም።
መካከለኛ የበሰለ ሙዝ፡ በጣም ጥቂት ወይም ምንም የሚባል አልኮል የለውም።
የጠቆረ (Overripe) ሙዝ፡ በተፈጥሯዊ መብላላት ምክንያት በውስጡ መጠነኛ አልኮል ይፈጠራል።
ልብ ሊባል የሚገባው፦
ይህ አልኮል ሙዙ ሲበስል ወይም በሙቀት ሲገነፍል ይበናል (Evaporate ያደርጋል)። ስለዚህ እነዚህን ሙዞች ለጥሬ አመጋገብ ከመጠቀም ይልቅ ለኬክ፣ ለዳቦ ወይም ለተለያዩ የዱቄት ምግቦች ማጣፈጫነት ቢጠቀሙባቸው ይመረጣል።
seledadotio
seledadotio
6 months ago
በጣም የቆዩ (የጠቆሩ) ሙዞችን ለልጆች ከመስጠት ይቆጠቡ!
ብዙዎቻችን ሙዝ በበሰለ ቁጥር ይጣፍጣል ብለን እናስባለን፤ ነገር ግን ከመጠን በላይ የበሰሉ እና የጠቆሩ ሙዞች ለልጆች ጤና ተስማሚ ላይሆኑ እንደሚችሉ ያውቃሉ?
ምክንያቱም፦
በሙዝ ውስጥ የሚገኘው የተፈጥሮ ስኳር እየቆየ ሲሄድ Natural Fermentation (ተፈጥሯዊ መብላላት) ይካሄዳል። በዚህም ምክንያት፦
ጥሬ (አረንጓዴ) ሙዝ፡ ምንም ዓይነት አልኮል የለውም።
መካከለኛ የበሰለ ሙዝ፡ በጣም ጥቂት ወይም ምንም የሚባል አልኮል የለውም።
የጠቆረ (Overripe) ሙዝ፡ በተፈጥሯዊ መብላላት ምክንያት በውስጡ መጠነኛ አልኮል ይፈጠራል።
ልብ ሊባል የሚገባው፦
ይህ አልኮል ሙዙ ሲበስል ወይም በሙቀት ሲገነፍል ይበናል (Evaporate ያደርጋል)። ስለዚህ እነዚህን ሙዞች ለጥሬ አመጋገብ ከመጠቀም ይልቅ ለኬክ፣ ለዳቦ ወይም ለተለያዩ የዱቄት ምግቦች ማጣፈጫነት ቢጠቀሙባቸው ይመረጣል።
ብዙዎቻችን ሙዝ በበሰለ ቁጥር ይጣፍጣል ብለን እናስባለን፤ ነገር ግን ከመጠን በላይ የበሰሉ እና የጠቆሩ ሙዞች ለልጆች ጤና ተስማሚ ላይሆኑ እንደሚችሉ ያውቃሉ?
ምክንያቱም፦
በሙዝ ውስጥ የሚገኘው የተፈጥሮ ስኳር እየቆየ ሲሄድ Natural Fermentation (ተፈጥሯዊ መብላላት) ይካሄዳል። በዚህም ምክንያት፦
ጥሬ (አረንጓዴ) ሙዝ፡ ምንም ዓይነት አልኮል የለውም።
መካከለኛ የበሰለ ሙዝ፡ በጣም ጥቂት ወይም ምንም የሚባል አልኮል የለውም።
የጠቆረ (Overripe) ሙዝ፡ በተፈጥሯዊ መብላላት ምክንያት በውስጡ መጠነኛ አልኮል ይፈጠራል።
ልብ ሊባል የሚገባው፦
ይህ አልኮል ሙዙ ሲበስል ወይም በሙቀት ሲገነፍል ይበናል (Evaporate ያደርጋል)። ስለዚህ እነዚህን ሙዞች ለጥሬ አመጋገብ ከመጠቀም ይልቅ ለኬክ፣ ለዳቦ ወይም ለተለያዩ የዱቄት ምግቦች ማጣፈጫነት ቢጠቀሙባቸው ይመረጣል።
6 months ago
የወዳጅነት ቀውስ፦ ጓደኝነትን መቼ እና እንዴት ማቆም አለብን?
የሰው ልጅ ማህበራዊ ፍጡር እንደመሆኑ መጠን ወዳጅነት የህይወቱ የጀርባ አጥንት ነው። ሆኖም ግን፣ ሁሉም የጓደኝነት ግንኙነቶች ለዘላለም አይዘልቁም። አንዳንድ ጊዜ በጊዜ ሂደት ወዳጅነት ሸክም ይሆናል፤ ደስታን ከመስጠት ይልቅ ቁጭትንና ንዴትን ያተርፋል። ታዲያ ይህን ቀውስ እንዴት እንወጣው?
ሳይኮሎጂስት ሙሪየል በትገር እና ታላላቅ ፈላስፎች በዚህ ጉዳይ ላይ ምን ይላሉ?
የጓደኝነት ተፈጥሮ እና የለውጥ አስፈላጊነት
ብዙዎቻችን ጓደኝነት አንዴ ከተጀመረ እስከ መቃብር መዝለቅ አለበት ብለን እናምናለን። ይህ ግን ሁልጊዜ እውነት አይደለም። የግሪክ ፈላስፋው አሪስጣጣሊስ ስለ ጓደኝነት ሲናገር ሦስት አይነት ወዳጅነቶችን ይለያል፡-
የጥቅም ወዳጅነት (Friendship of Utility)
የደስታ ወዳጅነት (Friendship of Pleasure)
የመልካምነት ወዳጅነት (Friendship of Virtue)
እንደ አሪስጣጣሊስ አባባል፣ የመጀመሪያዎቹ ሁለቱ ጓደኝነቶች ጥቅሙ ሲቀር ወይም ደስታው ሲጠፋ አብረው ይከስማሉ። የመጨረሻው ግን በባህሪ መመሳሰል ላይ የተመሰረተ ስለሆነ ረጅም ዕድሜ ይኖረዋል።
ሳይኮሎጂስት ሙሪየል በትገር እንደሚሉት፣ ጓደኝነት የሚለወጥባቸው በርካታ ምክንያቶች አሉ። "የጋራ መግባቢያ የነበሩ ነገሮች ሲጠፉ ግንኙነቱ መላላቱ አይቀሬ ነው" ይላሉ። ለምሳሌ ትምህርት መጨረስ፣ ስራ መቀየር፣ ወይም ወደ ሌላ ከተማ መሄድ ግንኙነትን ያቀዘቅዛሉ።
በተጨማሪም የህይወት ምዕራፎች መለዋወጥ (አንዱ ልጅ ሲወልድ ሌላው በብቸኝነት ነፃነቱን ሲያጣጥም) በመካከላቸው ያለውን ግንኙነት ፈታኝ ያደርገዋል።
ቀውሱ ሲከሰት ምን እናድርግ?
በጓደኝነትዎ ውስጥ ክፍተት ከተፈጠረ ግን ደግሞ ጓደኛዎን አሁንም የሚወዱት ከሆነ፣ ግንኙነቱን ለማስተካከል ጥረት ማድረግ ይቻላል። በትገር የሚከተሉትን ነጥቦች ይጠቁማሉ፡-
ራስን መመርመር፦ ምን አይነት ለውጥ እንዲመጣ እፈልጋለሁ? የእኔስ አስተዋጽኦ ምንድነው?
ክፍት ውይይት፦ "እኔ" በሚሉ አረፍተ ነገሮች ስሜትን መግለጽ። ለምሳሌ፦ "እኛ ብዙ ጊዜ አለመገናኘታችን እያሳሰበኝ ነው" ማለት በሌላው ሰው ላይ ጣት ከመቀሰር ይሻላል።
አድናቆትን መግለጽ፦ ውይይቱን የምናደርገው ጓደኝነቱ ስለሚቆረቁረን መሆኑን ማስረዳት ተገቢ ነው። "ይህንን የማወራህ ጓደኝነታችን ትልቅ ዋጋ ስላለው ነው" ማለት የተፈጠረውን ቅሬታ ወደ አዎንታዊ ግንኙነት ይለውጠዋል።
ታዋቂው ጀርመናዊ ፈላስፋ ፍሬድሪክ ኒቼ እንዲህ ብሏል፦ "ጓደኝነት የጋራ ስሜት ሳይሆን፣ የጋራ አመለካከትና የጋራ ግብ መኖር ነው"።
ጓደኛዎ የእርስዎን አዲስ ማንነት የማይቀበል ከሆነ ወይም በጋራ ግብ ላይ ካልሆናችሁ፣ ግንኙነቱ መቋረጡ ለሁለታችሁም ሰላም ሊሆን ይችላል።
ጓደኝነትን ማቆም፦ መቼ እና እንዴት?
አንዳንድ ጊዜ ጓደኝነትን ማቆም "ራዲካል" ወይም ጥብቅ የሆነ ውሳኔ ሊጠይቅ ይችላል። ግንኙነቱ በደስታ ፋንታ ጭንቀት የሚፈጥርብዎት ከሆነ፣ ለመለያየት ጊዜው አሁን ነው።
ሮማዊው ፈላስፋ ሴኔካ እንዲህ ይላል፦ "ከመጥፎ ሰዎች ጋር ከመቀመጥ ይልቅ ለብቻ መሆን ይሻላል"። ጓደኝነትዎ የእርስዎን እድገት የሚያደናቅፍ ወይም ስነ-ልቦናዊ ጫና የሚፈጥር ከሆነ እሱን መተው የራስን ደህንነት የመጠበቅ ጉዳይ ነው።
ሙሪየል በትገር ጓደኝነትን ለማቆም በሚደረግ ውይይት ወቅት የሚከተሉትን ጥንቃቄዎች ይመክራሉ፡-
ሰዓትና ቦታ መምረጥ፦ ጓደኛዎ በፈተና ወይም በስራ ውጥረት ላይ ባለበት ወቅት እንዲህ አይነት ውይይት አይጀምሩ።
ጫና አለመፍጠር፦ "ከሁለት ሳምንት በኋላ ወሳኝ ነገር እናወራለን" ብሎ ቀጠሮ መያዝ ሌላውን ሰው ያስጨንቃል። ይልቅስ ዘና ባለ ሁኔታ ውይይቱን መጀመር ይሻላል።
የአዕምሮ ዝግጅት፦ ከመነጋገራችሁ በፊት ትንፋሽን የመቆጣጠር ልምምድ (Mindfulness) ማድረግ ወይም ሃሳብን በወረቀት ላይ ማስፈር ለተረጋጋ ውይይት ይረዳል።
ማጠቃለያ
ጓደኝነት እንደ ወይን ነው፤ አንዳንድ ጊዜ በጊዜ ሂደት ይጣፍጣል፣ አንዳንዴ ግን ይኮመጥጣል። ፈረንሳዊው ፈላስፋ ሚሼል ደ ሞንቴኝ እንደገለጸው፣ እውነተኛ ጓደኝነት "ምክንያቱም እሱ እሱ ስለነበረ፣ እኔም እኔ ስለነበርኩ" የሚፈጠር ጥልቅ ትስስር ነው።
ይህ ትስስር ሲላላ ወይም ሲበጠስ ማዘን ተፈጥሯዊ ቢሆንም፣ የህይወት ጉዞ ግን ይቀጥላል።
አሮጌውን ጓደኝነት በክብር መሸኘት አዳዲስና የተሻሉ ግንኙነቶችን ለመመስረት በር ይከፍታል። ጤናማ ያልሆነ ግንኙነትን ይዞ ከመጓዝ፣ ትዝታውን ብቻ ይዞ መለየት ለሁለቱም ወገን ነፃነትን ይሰጣል።
የሰው ልጅ ማህበራዊ ፍጡር እንደመሆኑ መጠን ወዳጅነት የህይወቱ የጀርባ አጥንት ነው። ሆኖም ግን፣ ሁሉም የጓደኝነት ግንኙነቶች ለዘላለም አይዘልቁም። አንዳንድ ጊዜ በጊዜ ሂደት ወዳጅነት ሸክም ይሆናል፤ ደስታን ከመስጠት ይልቅ ቁጭትንና ንዴትን ያተርፋል። ታዲያ ይህን ቀውስ እንዴት እንወጣው?
ሳይኮሎጂስት ሙሪየል በትገር እና ታላላቅ ፈላስፎች በዚህ ጉዳይ ላይ ምን ይላሉ?
የጓደኝነት ተፈጥሮ እና የለውጥ አስፈላጊነት
ብዙዎቻችን ጓደኝነት አንዴ ከተጀመረ እስከ መቃብር መዝለቅ አለበት ብለን እናምናለን። ይህ ግን ሁልጊዜ እውነት አይደለም። የግሪክ ፈላስፋው አሪስጣጣሊስ ስለ ጓደኝነት ሲናገር ሦስት አይነት ወዳጅነቶችን ይለያል፡-
የጥቅም ወዳጅነት (Friendship of Utility)
የደስታ ወዳጅነት (Friendship of Pleasure)
የመልካምነት ወዳጅነት (Friendship of Virtue)
እንደ አሪስጣጣሊስ አባባል፣ የመጀመሪያዎቹ ሁለቱ ጓደኝነቶች ጥቅሙ ሲቀር ወይም ደስታው ሲጠፋ አብረው ይከስማሉ። የመጨረሻው ግን በባህሪ መመሳሰል ላይ የተመሰረተ ስለሆነ ረጅም ዕድሜ ይኖረዋል።
ሳይኮሎጂስት ሙሪየል በትገር እንደሚሉት፣ ጓደኝነት የሚለወጥባቸው በርካታ ምክንያቶች አሉ። "የጋራ መግባቢያ የነበሩ ነገሮች ሲጠፉ ግንኙነቱ መላላቱ አይቀሬ ነው" ይላሉ። ለምሳሌ ትምህርት መጨረስ፣ ስራ መቀየር፣ ወይም ወደ ሌላ ከተማ መሄድ ግንኙነትን ያቀዘቅዛሉ።
በተጨማሪም የህይወት ምዕራፎች መለዋወጥ (አንዱ ልጅ ሲወልድ ሌላው በብቸኝነት ነፃነቱን ሲያጣጥም) በመካከላቸው ያለውን ግንኙነት ፈታኝ ያደርገዋል።
ቀውሱ ሲከሰት ምን እናድርግ?
በጓደኝነትዎ ውስጥ ክፍተት ከተፈጠረ ግን ደግሞ ጓደኛዎን አሁንም የሚወዱት ከሆነ፣ ግንኙነቱን ለማስተካከል ጥረት ማድረግ ይቻላል። በትገር የሚከተሉትን ነጥቦች ይጠቁማሉ፡-
ራስን መመርመር፦ ምን አይነት ለውጥ እንዲመጣ እፈልጋለሁ? የእኔስ አስተዋጽኦ ምንድነው?
ክፍት ውይይት፦ "እኔ" በሚሉ አረፍተ ነገሮች ስሜትን መግለጽ። ለምሳሌ፦ "እኛ ብዙ ጊዜ አለመገናኘታችን እያሳሰበኝ ነው" ማለት በሌላው ሰው ላይ ጣት ከመቀሰር ይሻላል።
አድናቆትን መግለጽ፦ ውይይቱን የምናደርገው ጓደኝነቱ ስለሚቆረቁረን መሆኑን ማስረዳት ተገቢ ነው። "ይህንን የማወራህ ጓደኝነታችን ትልቅ ዋጋ ስላለው ነው" ማለት የተፈጠረውን ቅሬታ ወደ አዎንታዊ ግንኙነት ይለውጠዋል።
ታዋቂው ጀርመናዊ ፈላስፋ ፍሬድሪክ ኒቼ እንዲህ ብሏል፦ "ጓደኝነት የጋራ ስሜት ሳይሆን፣ የጋራ አመለካከትና የጋራ ግብ መኖር ነው"።
ጓደኛዎ የእርስዎን አዲስ ማንነት የማይቀበል ከሆነ ወይም በጋራ ግብ ላይ ካልሆናችሁ፣ ግንኙነቱ መቋረጡ ለሁለታችሁም ሰላም ሊሆን ይችላል።
ጓደኝነትን ማቆም፦ መቼ እና እንዴት?
አንዳንድ ጊዜ ጓደኝነትን ማቆም "ራዲካል" ወይም ጥብቅ የሆነ ውሳኔ ሊጠይቅ ይችላል። ግንኙነቱ በደስታ ፋንታ ጭንቀት የሚፈጥርብዎት ከሆነ፣ ለመለያየት ጊዜው አሁን ነው።
ሮማዊው ፈላስፋ ሴኔካ እንዲህ ይላል፦ "ከመጥፎ ሰዎች ጋር ከመቀመጥ ይልቅ ለብቻ መሆን ይሻላል"። ጓደኝነትዎ የእርስዎን እድገት የሚያደናቅፍ ወይም ስነ-ልቦናዊ ጫና የሚፈጥር ከሆነ እሱን መተው የራስን ደህንነት የመጠበቅ ጉዳይ ነው።
ሙሪየል በትገር ጓደኝነትን ለማቆም በሚደረግ ውይይት ወቅት የሚከተሉትን ጥንቃቄዎች ይመክራሉ፡-
ሰዓትና ቦታ መምረጥ፦ ጓደኛዎ በፈተና ወይም በስራ ውጥረት ላይ ባለበት ወቅት እንዲህ አይነት ውይይት አይጀምሩ።
ጫና አለመፍጠር፦ "ከሁለት ሳምንት በኋላ ወሳኝ ነገር እናወራለን" ብሎ ቀጠሮ መያዝ ሌላውን ሰው ያስጨንቃል። ይልቅስ ዘና ባለ ሁኔታ ውይይቱን መጀመር ይሻላል።
የአዕምሮ ዝግጅት፦ ከመነጋገራችሁ በፊት ትንፋሽን የመቆጣጠር ልምምድ (Mindfulness) ማድረግ ወይም ሃሳብን በወረቀት ላይ ማስፈር ለተረጋጋ ውይይት ይረዳል።
ማጠቃለያ
ጓደኝነት እንደ ወይን ነው፤ አንዳንድ ጊዜ በጊዜ ሂደት ይጣፍጣል፣ አንዳንዴ ግን ይኮመጥጣል። ፈረንሳዊው ፈላስፋ ሚሼል ደ ሞንቴኝ እንደገለጸው፣ እውነተኛ ጓደኝነት "ምክንያቱም እሱ እሱ ስለነበረ፣ እኔም እኔ ስለነበርኩ" የሚፈጠር ጥልቅ ትስስር ነው።
ይህ ትስስር ሲላላ ወይም ሲበጠስ ማዘን ተፈጥሯዊ ቢሆንም፣ የህይወት ጉዞ ግን ይቀጥላል።
አሮጌውን ጓደኝነት በክብር መሸኘት አዳዲስና የተሻሉ ግንኙነቶችን ለመመስረት በር ይከፍታል። ጤናማ ያልሆነ ግንኙነትን ይዞ ከመጓዝ፣ ትዝታውን ብቻ ይዞ መለየት ለሁለቱም ወገን ነፃነትን ይሰጣል።
7 months ago
🧠 ከፍተኛ IQ እና የብቸኝነት ምስጢር፡ ለምንድነው ብልህ መሆን ለፍቅር ግንኙነት ፈታኝ የሆነው?
ብዙዎቻችን ብልህ መሆን በሁሉም የህይወት ዘርፍ ስኬታማ ያደርጋል ብለን እናስባለን። ነገር ግን በጥናት የተረጋገጠው እውነታ ሌላ ነው፤ ከፍተኛ የማሰብ ችሎታ (High IQ) ያላቸው ሰዎች በፍቅር ግንኙነት የመቀጠል እድላቸው ዝቅተኛ መሆኑ ተስተውሏል።
1. "ትንታኔ ሽባ ያደርጋል" (Analysis Paralysis)
አስተዋይ ሰዎች አንድን ግንኙነት ከመጀመራቸው በፊት ሊመጡ የሚችሉ ችግሮችን አስቀድመው ለመተንተን ይሞክራሉ። "ወደፊት ቢለየኝስ?" ወይም "ባይስማማንስ?" በሚል ስጋት ውስጥ ስለሚገቡ፣ ስሜታቸውን በነፃነት መልቀቅ ይከብዳቸዋል።
2. ነጻነትን ማክበር (Valuing Independence)
ከፍተኛ IQ ያላቸው ሰዎች ብቸኝነትን አይፈሩም። የራሳቸውን ጊዜ፣ ንባብ እና ምርምር ስለሚወዱ፣ አንድ ሰው ህይወታቸው ውስጥ ገብቶ የግል ነጻነታቸውን ሲጋፋቸው ግንኙነቱን ከማስተካከል ይልቅ ብቸኝነትን መምረጥ ይቀላቸዋል።
3. በስሜት (EQ) እና በዕውቀት (IQ) መካከል ያለው ልዩነት
ብዙውን ጊዜ ከፍተኛ የ IQ ደረጃ ያላቸው ሰዎች፣ ስሜታዊ ብልህነታቸው ዝቅተኛ ሊሆን ይችላል።
ይህ ደግሞ የትዳር አጋራቸውን ስሜት በቃላት ሳይነገራቸው በደመነፍስ ለመረዳት እንዲቸገሩ ያደርጋቸዋል።
4. "Sapiosexuality" (የአዕምሮ ብስለት ፍለጋ)
እነዚህ ሰዎች የሚሳቡት በአካል ውበት ሳይሆን በአዕምሮ ብስለት ነው። በንግግር ሊያሸንፋቸው የሚችል ሰው ማግኘት ደግሞ በዘመናችን እጅግ ብርቅ እየሆነ በመምጣቱ ብቸኝነታቸው ይረዝማል።
💡 ማጠቃለያ፦
ብልህነት በራሱ ችግር ባይሆንም፣ ፍቅር ደግሞ ከጭንቅላት ይልቅ የልብ ስራ በመሆኑ ሁለቱን ማመጣጠን ትልቅ ጥበብን ይጠይቃል።
seledadotio
ብዙዎቻችን ብልህ መሆን በሁሉም የህይወት ዘርፍ ስኬታማ ያደርጋል ብለን እናስባለን። ነገር ግን በጥናት የተረጋገጠው እውነታ ሌላ ነው፤ ከፍተኛ የማሰብ ችሎታ (High IQ) ያላቸው ሰዎች በፍቅር ግንኙነት የመቀጠል እድላቸው ዝቅተኛ መሆኑ ተስተውሏል።
1. "ትንታኔ ሽባ ያደርጋል" (Analysis Paralysis)
አስተዋይ ሰዎች አንድን ግንኙነት ከመጀመራቸው በፊት ሊመጡ የሚችሉ ችግሮችን አስቀድመው ለመተንተን ይሞክራሉ። "ወደፊት ቢለየኝስ?" ወይም "ባይስማማንስ?" በሚል ስጋት ውስጥ ስለሚገቡ፣ ስሜታቸውን በነፃነት መልቀቅ ይከብዳቸዋል።
2. ነጻነትን ማክበር (Valuing Independence)
ከፍተኛ IQ ያላቸው ሰዎች ብቸኝነትን አይፈሩም። የራሳቸውን ጊዜ፣ ንባብ እና ምርምር ስለሚወዱ፣ አንድ ሰው ህይወታቸው ውስጥ ገብቶ የግል ነጻነታቸውን ሲጋፋቸው ግንኙነቱን ከማስተካከል ይልቅ ብቸኝነትን መምረጥ ይቀላቸዋል።
3. በስሜት (EQ) እና በዕውቀት (IQ) መካከል ያለው ልዩነት
ብዙውን ጊዜ ከፍተኛ የ IQ ደረጃ ያላቸው ሰዎች፣ ስሜታዊ ብልህነታቸው ዝቅተኛ ሊሆን ይችላል።
ይህ ደግሞ የትዳር አጋራቸውን ስሜት በቃላት ሳይነገራቸው በደመነፍስ ለመረዳት እንዲቸገሩ ያደርጋቸዋል።
4. "Sapiosexuality" (የአዕምሮ ብስለት ፍለጋ)
እነዚህ ሰዎች የሚሳቡት በአካል ውበት ሳይሆን በአዕምሮ ብስለት ነው። በንግግር ሊያሸንፋቸው የሚችል ሰው ማግኘት ደግሞ በዘመናችን እጅግ ብርቅ እየሆነ በመምጣቱ ብቸኝነታቸው ይረዝማል።
💡 ማጠቃለያ፦
ብልህነት በራሱ ችግር ባይሆንም፣ ፍቅር ደግሞ ከጭንቅላት ይልቅ የልብ ስራ በመሆኑ ሁለቱን ማመጣጠን ትልቅ ጥበብን ይጠይቃል።
seledadotio
Sponsored by
Surafel
7 months ago
🧠 ከፍተኛ IQ እና የብቸኝነት ምስጢር፡ ለምንድነው ብልህ መሆን ለፍቅር ግንኙነት ፈታኝ የሆነው?
ብዙዎቻችን ብልህ መሆን በሁሉም የህይወት ዘርፍ ስኬታማ ያደርጋል ብለን እናስባለን። ነገር ግን በጥናት የተረጋገጠው እውነታ ሌላ ነው፤ ከፍተኛ የማሰብ ችሎታ (High IQ) ያላቸው ሰዎች በፍቅር ግንኙነት የመቀጠል እድላቸው ዝቅተኛ መሆኑ ተስተውሏል።
1. "ትንታኔ ሽባ ያደርጋል" (Analysis Paralysis)
አስተዋይ ሰዎች አንድን ግንኙነት ከመጀመራቸው በፊት ሊመጡ የሚችሉ ችግሮችን አስቀድመው ለመተንተን ይሞክራሉ። "ወደፊት ቢለየኝስ?" ወይም "ባይስማማንስ?" በሚል ስጋት ውስጥ ስለሚገቡ፣ ስሜታቸውን በነፃነት መልቀቅ ይከብዳቸዋል።
2. ነጻነትን ማክበር (Valuing Independence)
ከፍተኛ IQ ያላቸው ሰዎች ብቸኝነትን አይፈሩም። የራሳቸውን ጊዜ፣ ንባብ እና ምርምር ስለሚወዱ፣ አንድ ሰው ህይወታቸው ውስጥ ገብቶ የግል ነጻነታቸውን ሲጋፋቸው ግንኙነቱን ከማስተካከል ይልቅ ብቸኝነትን መምረጥ ይቀላቸዋል።
3. በስሜት (EQ) እና በዕውቀት (IQ) መካከል ያለው ልዩነት
ብዙውን ጊዜ ከፍተኛ የ IQ ደረጃ ያላቸው ሰዎች፣ ስሜታዊ ብልህነታቸው ዝቅተኛ ሊሆን ይችላል።
ይህ ደግሞ የትዳር አጋራቸውን ስሜት በቃላት ሳይነገራቸው በደመነፍስ ለመረዳት እንዲቸገሩ ያደርጋቸዋል።
4. "Sapiosexuality" (የአዕምሮ ብስለት ፍለጋ)
እነዚህ ሰዎች የሚሳቡት በአካል ውበት ሳይሆን በአዕምሮ ብስለት ነው። በንግግር ሊያሸንፋቸው የሚችል ሰው ማግኘት ደግሞ በዘመናችን እጅግ ብርቅ እየሆነ በመምጣቱ ብቸኝነታቸው ይረዝማል።
💡 ማጠቃለያ፦
ብልህነት በራሱ ችግር ባይሆንም፣ ፍቅር ደግሞ ከጭንቅላት ይልቅ የልብ ስራ በመሆኑ ሁለቱን ማመጣጠን ትልቅ ጥበብን ይጠይቃል።
ብዙዎቻችን ብልህ መሆን በሁሉም የህይወት ዘርፍ ስኬታማ ያደርጋል ብለን እናስባለን። ነገር ግን በጥናት የተረጋገጠው እውነታ ሌላ ነው፤ ከፍተኛ የማሰብ ችሎታ (High IQ) ያላቸው ሰዎች በፍቅር ግንኙነት የመቀጠል እድላቸው ዝቅተኛ መሆኑ ተስተውሏል።
1. "ትንታኔ ሽባ ያደርጋል" (Analysis Paralysis)
አስተዋይ ሰዎች አንድን ግንኙነት ከመጀመራቸው በፊት ሊመጡ የሚችሉ ችግሮችን አስቀድመው ለመተንተን ይሞክራሉ። "ወደፊት ቢለየኝስ?" ወይም "ባይስማማንስ?" በሚል ስጋት ውስጥ ስለሚገቡ፣ ስሜታቸውን በነፃነት መልቀቅ ይከብዳቸዋል።
2. ነጻነትን ማክበር (Valuing Independence)
ከፍተኛ IQ ያላቸው ሰዎች ብቸኝነትን አይፈሩም። የራሳቸውን ጊዜ፣ ንባብ እና ምርምር ስለሚወዱ፣ አንድ ሰው ህይወታቸው ውስጥ ገብቶ የግል ነጻነታቸውን ሲጋፋቸው ግንኙነቱን ከማስተካከል ይልቅ ብቸኝነትን መምረጥ ይቀላቸዋል።
3. በስሜት (EQ) እና በዕውቀት (IQ) መካከል ያለው ልዩነት
ብዙውን ጊዜ ከፍተኛ የ IQ ደረጃ ያላቸው ሰዎች፣ ስሜታዊ ብልህነታቸው ዝቅተኛ ሊሆን ይችላል።
ይህ ደግሞ የትዳር አጋራቸውን ስሜት በቃላት ሳይነገራቸው በደመነፍስ ለመረዳት እንዲቸገሩ ያደርጋቸዋል።
4. "Sapiosexuality" (የአዕምሮ ብስለት ፍለጋ)
እነዚህ ሰዎች የሚሳቡት በአካል ውበት ሳይሆን በአዕምሮ ብስለት ነው። በንግግር ሊያሸንፋቸው የሚችል ሰው ማግኘት ደግሞ በዘመናችን እጅግ ብርቅ እየሆነ በመምጣቱ ብቸኝነታቸው ይረዝማል።
💡 ማጠቃለያ፦
ብልህነት በራሱ ችግር ባይሆንም፣ ፍቅር ደግሞ ከጭንቅላት ይልቅ የልብ ስራ በመሆኑ ሁለቱን ማመጣጠን ትልቅ ጥበብን ይጠይቃል።
7 months ago
🥦 ከብሮኮሊ በላይ አስገራሚው አትክልት የትኛው እንደሆነ ያውቃሉ?
ብዙዎቻችን ብሮኮሊ በአልሚ ምግብ ይዘቱ ቀዳሚ ይመስሉናል፤ ነገር ግን ሳይንሳዊ ግኝቶች ሌላ አስገራሚ ውጤት ይዘው መጥተዋል።
የአሜሪካው የበሽታ መቆጣጠሪያና መከላከያ ማዕከል (CDC) በ41 የአትክልትና ፍራፍሬ አይነቶች ላይ ጥልቅ ጥናት አድርጓል። በጥናቱም ንጥረ-ነገራቸው ከፍተኛ ሆኖ ካሎሪያቸው ዝቅተኛ የሆኑትን ዝርዝር አውጥቷል።
የጥናቱ ውጤት እንዲህ ይላል፦
🏅 የውሃ ፌጦ (Watercress): በዝርዝሩ ውስጥ ብቸኛው 100/100 ሙሉ ነጥብ ያገኘ ቁንጮ አትክልት ነው።
🔹 በአንድ ኩባያ ውስጥ ብቻ የቀኑን 106% ቫይታሚን K እና ከፍተኛ ቫይታሚን C ይዟል።
🔹 የካሎሪ መጠኑ እጅግ ዝቅተኛ (4 kcal) ሲሆን፣ ለሰውነት ግን ሙሉ ጉልበትና የበሽታ መከላከል አቅም ይሰጣል።
🥦 ብሮኮሊ (Broccoli): ለጤና እጅግ አስፈላጊ ቢሆንም፣ በንጥረ-ነገር ክምችቱ ያገኘው ነጥብ 34.89 ነው።
🍅 ቲማቲም: በፍራፍሬዎች ዝርዝር ውስጥ ቀዳሚ ቢሆንም፣ ያገኘው ነጥብ 20.37 ብቻ ነው።
ለማጠቃለል፦ ጤናማ ለመሆን የተለያዩ አትክልቶችን ማዘውተር ቢመከርም፣ ዋተርክሬስን ግን የአመጋገብዎ አካል ቢያደርጉት እጥፍ ትርፍ ያገኛሉ!
ብዙዎቻችን ብሮኮሊ በአልሚ ምግብ ይዘቱ ቀዳሚ ይመስሉናል፤ ነገር ግን ሳይንሳዊ ግኝቶች ሌላ አስገራሚ ውጤት ይዘው መጥተዋል።
የአሜሪካው የበሽታ መቆጣጠሪያና መከላከያ ማዕከል (CDC) በ41 የአትክልትና ፍራፍሬ አይነቶች ላይ ጥልቅ ጥናት አድርጓል። በጥናቱም ንጥረ-ነገራቸው ከፍተኛ ሆኖ ካሎሪያቸው ዝቅተኛ የሆኑትን ዝርዝር አውጥቷል።
የጥናቱ ውጤት እንዲህ ይላል፦
🏅 የውሃ ፌጦ (Watercress): በዝርዝሩ ውስጥ ብቸኛው 100/100 ሙሉ ነጥብ ያገኘ ቁንጮ አትክልት ነው።
🔹 በአንድ ኩባያ ውስጥ ብቻ የቀኑን 106% ቫይታሚን K እና ከፍተኛ ቫይታሚን C ይዟል።
🔹 የካሎሪ መጠኑ እጅግ ዝቅተኛ (4 kcal) ሲሆን፣ ለሰውነት ግን ሙሉ ጉልበትና የበሽታ መከላከል አቅም ይሰጣል።
🥦 ብሮኮሊ (Broccoli): ለጤና እጅግ አስፈላጊ ቢሆንም፣ በንጥረ-ነገር ክምችቱ ያገኘው ነጥብ 34.89 ነው።
🍅 ቲማቲም: በፍራፍሬዎች ዝርዝር ውስጥ ቀዳሚ ቢሆንም፣ ያገኘው ነጥብ 20.37 ብቻ ነው።
ለማጠቃለል፦ ጤናማ ለመሆን የተለያዩ አትክልቶችን ማዘውተር ቢመከርም፣ ዋተርክሬስን ግን የአመጋገብዎ አካል ቢያደርጉት እጥፍ ትርፍ ያገኛሉ!
7 months ago
ዓለም ላይ ከሚሸጡ የታሸጉ ውሃዎች ውስጥ ግማሽ የሚሆኑት ከቧንቧ የተቀዳ ውሃ መሆናቸውን ያውቃሉ?
ብዙዎቻችን የታሸጉ ውሃዎች የሚመጡት ከንፁህ የተፈጥሮ ምንጮች ወይም ከተራራዎች እንደሆነ ብናስብም፣ እውነታው ግን ከዚህ የተለየ ነው። የታሸጉ ውሃ አምራቾች ከተራ የቧንቧ ውሃ ላይ ማጣሪያ በማድረግና አንዳንድ ማዕድናትን በመጨመር መልሰው ያሽጉታል።
በአሜሪካ ውስጥ ደግሞ ወደ 64% የሚጠጋ የታሸገ ውሃ የቧንቧ ውሃ ብቻ መሆኑን አንድ ጥናት አመልክቷል።
seledadotio
seledadotio
ብዙዎቻችን የታሸጉ ውሃዎች የሚመጡት ከንፁህ የተፈጥሮ ምንጮች ወይም ከተራራዎች እንደሆነ ብናስብም፣ እውነታው ግን ከዚህ የተለየ ነው። የታሸጉ ውሃ አምራቾች ከተራ የቧንቧ ውሃ ላይ ማጣሪያ በማድረግና አንዳንድ ማዕድናትን በመጨመር መልሰው ያሽጉታል።
በአሜሪካ ውስጥ ደግሞ ወደ 64% የሚጠጋ የታሸገ ውሃ የቧንቧ ውሃ ብቻ መሆኑን አንድ ጥናት አመልክቷል።
seledadotio
seledadotio
7 months ago
ለጤናማ ህይወት በቀን ስንት ሰዓት መተኛት አለብን?
ብዙዎቻችን "ጥሩ እንቅልፍ" ስንል ለሁሉም ሰው እኩል የሆነ ሰዓት ይመስለናል፤ ነገር ግን የእንቅልፍ ፍላጎት እንደ እድሜ እና እንደ ጤና ሁኔታ ይለያያል።
እንደ እድሜ ክልል የሚመከሩ የእንቅልፍ ሰዓታት፦
አዲስ የተወለዱ ህፃናት፦ በቀን ከ14 እስከ 17 ሰዓት
ተማሪዎች (ህፃናት)፦ በቀን ከ9 እስከ 12 ሰዓት
አፍላ ወጣቶች (Teenagers)፦ በቀን ከ8 እስከ 10 ሰዓት
አዋቂዎች፦ በቀን 7 እና ከዚያ በላይ ሰዓት
ጥቂት መተኛት ምን ጉዳት አለው?
አንድ አዋቂ ሰው በቀን ከ7 ሰዓት በታች አዘውትሮ የሚተኛ ከሆነ ለተለያዩ የጤና ችግሮች ሊጋለጥ ይችላል። ከነዚህም መካከል፦
👉ከመጠን ያለፈ ውፍረት
👉የስኳር በሽታ
👉የደም ግፊት እና የልብ ህመም
👉የአእምሮ ጭንቀት (Depression)
በእንቅልፍ ፍላጎት ላይ ተጽዕኖ የሚያሳድሩ ነገሮች፦
የእንቅልፍ ጥራት፦ እንቅልፍዎ የሚቆራረጥ ከሆነ ለረጅም ሰዓት ቢተኙም ሰውነትዎ አያርፍም።
የእንቅልፍ እዳ፦ ከዚህ ቀደም በቂ እንቅልፍ አጥተው ከሆነ፣ ሰውነትዎ ለማገገም ተጨማሪ ሰዓት ሊፈልግ ይችላል።
ነፍሰ ጡር፦ የሆርሞን ለውጥ እና አካላዊ ምቾት ማጣት ተጨማሪ እረፍት ያስፈልጋቸዋል።
እድሜ፦ አረጋውያን ልክ እንደ ወጣቶች ተመሳሳይ ሰዓት ቢፈልጉም፣ እንቅልፋቸው የመቅለል እና የመቆራረጥ ባህሪ ይኖረዋል።
ጥሩ እንቅልፍ ለልጆች የተሻለ ትኩረትና የማስታወስ ችሎታን ሲሰጥ፣ ለአዋቂዎች ደግሞ በሽታን የመከላከል አቅምን ያጠናክራል።
seledadotio
seledadotio
ብዙዎቻችን "ጥሩ እንቅልፍ" ስንል ለሁሉም ሰው እኩል የሆነ ሰዓት ይመስለናል፤ ነገር ግን የእንቅልፍ ፍላጎት እንደ እድሜ እና እንደ ጤና ሁኔታ ይለያያል።
እንደ እድሜ ክልል የሚመከሩ የእንቅልፍ ሰዓታት፦
አዲስ የተወለዱ ህፃናት፦ በቀን ከ14 እስከ 17 ሰዓት
ተማሪዎች (ህፃናት)፦ በቀን ከ9 እስከ 12 ሰዓት
አፍላ ወጣቶች (Teenagers)፦ በቀን ከ8 እስከ 10 ሰዓት
አዋቂዎች፦ በቀን 7 እና ከዚያ በላይ ሰዓት
ጥቂት መተኛት ምን ጉዳት አለው?
አንድ አዋቂ ሰው በቀን ከ7 ሰዓት በታች አዘውትሮ የሚተኛ ከሆነ ለተለያዩ የጤና ችግሮች ሊጋለጥ ይችላል። ከነዚህም መካከል፦
👉ከመጠን ያለፈ ውፍረት
👉የስኳር በሽታ
👉የደም ግፊት እና የልብ ህመም
👉የአእምሮ ጭንቀት (Depression)
በእንቅልፍ ፍላጎት ላይ ተጽዕኖ የሚያሳድሩ ነገሮች፦
የእንቅልፍ ጥራት፦ እንቅልፍዎ የሚቆራረጥ ከሆነ ለረጅም ሰዓት ቢተኙም ሰውነትዎ አያርፍም።
የእንቅልፍ እዳ፦ ከዚህ ቀደም በቂ እንቅልፍ አጥተው ከሆነ፣ ሰውነትዎ ለማገገም ተጨማሪ ሰዓት ሊፈልግ ይችላል።
ነፍሰ ጡር፦ የሆርሞን ለውጥ እና አካላዊ ምቾት ማጣት ተጨማሪ እረፍት ያስፈልጋቸዋል።
እድሜ፦ አረጋውያን ልክ እንደ ወጣቶች ተመሳሳይ ሰዓት ቢፈልጉም፣ እንቅልፋቸው የመቅለል እና የመቆራረጥ ባህሪ ይኖረዋል።
ጥሩ እንቅልፍ ለልጆች የተሻለ ትኩረትና የማስታወስ ችሎታን ሲሰጥ፣ ለአዋቂዎች ደግሞ በሽታን የመከላከል አቅምን ያጠናክራል።
seledadotio
seledadotio
7 months ago
ዓለም ላይ ከሚሸጡ የታሸጉ ውሃዎች ውስጥ ግማሽ የሚሆኑት ከቧንቧ የተቀዳ ውሃ መሆናቸውን ያውቃሉ?
ብዙዎቻችን የታሸጉ ውሃዎች የሚመጡት ከንፁህ የተፈጥሮ ምንጮች ወይም ከተራራዎች እንደሆነ ብናስብም፣ እውነታው ግን ከዚህ የተለየ ነው። የታሸጉ ውሃ አምራቾች ከተራ የቧንቧ ውሃ ላይ ማጣሪያ በማድረግና አንዳንድ ማዕድናትን በመጨመር መልሰው ያሽጉታል።
በአሜሪካ ውስጥ ደግሞ ወደ 64% የሚጠጋ የታሸገ ውሃ የቧንቧ ውሃ ብቻ መሆኑን አንድ ጥናት አመልክቷል።
ብዙዎቻችን የታሸጉ ውሃዎች የሚመጡት ከንፁህ የተፈጥሮ ምንጮች ወይም ከተራራዎች እንደሆነ ብናስብም፣ እውነታው ግን ከዚህ የተለየ ነው። የታሸጉ ውሃ አምራቾች ከተራ የቧንቧ ውሃ ላይ ማጣሪያ በማድረግና አንዳንድ ማዕድናትን በመጨመር መልሰው ያሽጉታል።
በአሜሪካ ውስጥ ደግሞ ወደ 64% የሚጠጋ የታሸገ ውሃ የቧንቧ ውሃ ብቻ መሆኑን አንድ ጥናት አመልክቷል።
Sponsored by
Surafel
7 months ago
ለጤናማ ህይወት በቀን ስንት ሰዓት መተኛት አለብን?
ብዙዎቻችን "ጥሩ እንቅልፍ" ስንል ለሁሉም ሰው እኩል የሆነ ሰዓት ይመስለናል፤ ነገር ግን የእንቅልፍ ፍላጎት እንደ እድሜ እና እንደ ጤና ሁኔታ ይለያያል።
እንደ እድሜ ክልል የሚመከሩ የእንቅልፍ ሰዓታት፦
አዲስ የተወለዱ ህፃናት፦ በቀን ከ14 እስከ 17 ሰዓት
ተማሪዎች (ህፃናት)፦ በቀን ከ9 እስከ 12 ሰዓት
አፍላ ወጣቶች (Teenagers)፦ በቀን ከ8 እስከ 10 ሰዓት
አዋቂዎች፦ በቀን 7 እና ከዚያ በላይ ሰዓት
ጥቂት መተኛት ምን ጉዳት አለው?
አንድ አዋቂ ሰው በቀን ከ7 ሰዓት በታች አዘውትሮ የሚተኛ ከሆነ ለተለያዩ የጤና ችግሮች ሊጋለጥ ይችላል። ከነዚህም መካከል፦
👉ከመጠን ያለፈ ውፍረት
👉የስኳር በሽታ
👉የደም ግፊት እና የልብ ህመም
👉የአእምሮ ጭንቀት (Depression)
በእንቅልፍ ፍላጎት ላይ ተጽዕኖ የሚያሳድሩ ነገሮች፦
የእንቅልፍ ጥራት፦ እንቅልፍዎ የሚቆራረጥ ከሆነ ለረጅም ሰዓት ቢተኙም ሰውነትዎ አያርፍም።
የእንቅልፍ እዳ፦ ከዚህ ቀደም በቂ እንቅልፍ አጥተው ከሆነ፣ ሰውነትዎ ለማገገም ተጨማሪ ሰዓት ሊፈልግ ይችላል።
ነፍሰ ጡር፦ የሆርሞን ለውጥ እና አካላዊ ምቾት ማጣት ተጨማሪ እረፍት ያስፈልጋቸዋል።
እድሜ፦ አረጋውያን ልክ እንደ ወጣቶች ተመሳሳይ ሰዓት ቢፈልጉም፣ እንቅልፋቸው የመቅለል እና የመቆራረጥ ባህሪ ይኖረዋል።
ጥሩ እንቅልፍ ለልጆች የተሻለ ትኩረትና የማስታወስ ችሎታን ሲሰጥ፣ ለአዋቂዎች ደግሞ በሽታን የመከላከል አቅምን ያጠናክራል።
ብዙዎቻችን "ጥሩ እንቅልፍ" ስንል ለሁሉም ሰው እኩል የሆነ ሰዓት ይመስለናል፤ ነገር ግን የእንቅልፍ ፍላጎት እንደ እድሜ እና እንደ ጤና ሁኔታ ይለያያል።
እንደ እድሜ ክልል የሚመከሩ የእንቅልፍ ሰዓታት፦
አዲስ የተወለዱ ህፃናት፦ በቀን ከ14 እስከ 17 ሰዓት
ተማሪዎች (ህፃናት)፦ በቀን ከ9 እስከ 12 ሰዓት
አፍላ ወጣቶች (Teenagers)፦ በቀን ከ8 እስከ 10 ሰዓት
አዋቂዎች፦ በቀን 7 እና ከዚያ በላይ ሰዓት
ጥቂት መተኛት ምን ጉዳት አለው?
አንድ አዋቂ ሰው በቀን ከ7 ሰዓት በታች አዘውትሮ የሚተኛ ከሆነ ለተለያዩ የጤና ችግሮች ሊጋለጥ ይችላል። ከነዚህም መካከል፦
👉ከመጠን ያለፈ ውፍረት
👉የስኳር በሽታ
👉የደም ግፊት እና የልብ ህመም
👉የአእምሮ ጭንቀት (Depression)
በእንቅልፍ ፍላጎት ላይ ተጽዕኖ የሚያሳድሩ ነገሮች፦
የእንቅልፍ ጥራት፦ እንቅልፍዎ የሚቆራረጥ ከሆነ ለረጅም ሰዓት ቢተኙም ሰውነትዎ አያርፍም።
የእንቅልፍ እዳ፦ ከዚህ ቀደም በቂ እንቅልፍ አጥተው ከሆነ፣ ሰውነትዎ ለማገገም ተጨማሪ ሰዓት ሊፈልግ ይችላል።
ነፍሰ ጡር፦ የሆርሞን ለውጥ እና አካላዊ ምቾት ማጣት ተጨማሪ እረፍት ያስፈልጋቸዋል።
እድሜ፦ አረጋውያን ልክ እንደ ወጣቶች ተመሳሳይ ሰዓት ቢፈልጉም፣ እንቅልፋቸው የመቅለል እና የመቆራረጥ ባህሪ ይኖረዋል።
ጥሩ እንቅልፍ ለልጆች የተሻለ ትኩረትና የማስታወስ ችሎታን ሲሰጥ፣ ለአዋቂዎች ደግሞ በሽታን የመከላከል አቅምን ያጠናክራል።
Comments