9 hours ago
ኢትዮጵያን ሊፈታተኑ የሚሞክሩ ኃይሎችን ድባቅ የሚመታ ጀግና አየር ኃይል ተገንብቷል - ሌ/ጄ ይልማ መርዳሳ‼️
ኢትዮጵያን ሊፈታተኑ የሚሞክሩ ኃይሎችን ድባቅ የሚመታ ጀግና አየር ኃይል ተገንብቷል አሉ የኢፌዴሪ አየር ኃይል አዛዥ ሌተናል ጄኔራል ይልማ መርዳሳ፡፡
የአየር ኃይሉ የ3ኛ አየር ምድብ ላስመዘገበው የላቀ የግዳጅና የሥራ አፈጻጸም ስኬት በድሬዳዋ ከተማ በሚገኘው የምድቡ ጠቅላይ መምሪያ የእውቅናና የምስጋና መርሐ ግብር ተካሂዷል፡፡
ሌተናል ጄኔራል ይልማ መርዳሳ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፥ መከላከያ ሠራዊት በሰው ኃይልና በቴክኖሎጂ ከፍተኛ ለውጥ እያደረገ ይገኛል፡፡
አሁን የምንገኝበት ዘመን የውጊያ አካሄድና ስልት ለመገመት በሚያዳግት መልኩ በፍጥነት እየተቀያየረ ነው ያሉት አዛዡ፥ ኢትዮጵያ በምትገኝበት ቀጣናም ያለው የኃይል አሰላለፍ ተለዋዋጭና ኢ-ተገማች መሆኑን ጠቁመዋል።
የኢፌዴሪ አየር ኃይልም ይህንን ታሳቢ በማድረግ የዘመኑን ቴክኖሎጂ መጠቀም የሚችል የሰው ኃይል በማብቃት፣ በርካታ ፓይለቶችን፣ ቴክኒሽያኖችንና የአስተዳደር ባለሙያዎች እያፈራ መሆኑንና የዘመኑን የውጊያ ቴክኖሎጂዎች እየታጠቀ እንደሚገኝ አረጋግጠዋል።
3ኛ አየር ምድብም የሪፎርሙ አካል በመሆን በርካታ ሥራዎችን በማከናወን ልዩ ታሪክ ያለው መሆኑንም አንስተዋል።
ምድቡ ኮሎኔል በዛብህ ጴጥሮስ እና ኮሎኔል ባጫ ሁንዴን የመሳሰሉ በርካታ ጀግኖችን ያፈራ መሆኑን አስታውሰው፥ አሁንም ያንን የጀግንነት ታሪክ እያደሰ በርካታ ተተኪ ወጣት በራሪዎችን በአጭር ጊዜ፣ በጥራትና በብዛት እያፈራ ይገኛል ነው ያሉት።
የሚለወጠውን የውጊያ አውድና የኃይል አሰላለፍ በመገንዘብ አመራሩና ሠራዊቱ ራሱን ከጊዜው ጋር ማዘመን እንዳለበት አስገንዝበዋል።
ኢትዮጵያን ሊፈታተኑ የሚሞክሩ ጠላቶችን መመከትና ድባቅ መምታት የሚያስችል ጀግና ተቋም መገንባቱን ገልጸው፥ የምድቡ አመራሮችና የሠራዊት አባላት ግዳጃቸውን በጀግንነትና በስኬት በመወጣታቸው ሊኮሩ ይገባል ብለዋል፡፡
በቀጣይም ታላላቅ ተልዕኮዎች እንደሚጠበቁ በመረዳት በሁሉም ረገድ ዝግጁነትን ማጠናከር እንደሚያስፈልግ ገልፀዋል።
Seledadotio
Seledadotio
ኢትዮጵያን ሊፈታተኑ የሚሞክሩ ኃይሎችን ድባቅ የሚመታ ጀግና አየር ኃይል ተገንብቷል አሉ የኢፌዴሪ አየር ኃይል አዛዥ ሌተናል ጄኔራል ይልማ መርዳሳ፡፡
የአየር ኃይሉ የ3ኛ አየር ምድብ ላስመዘገበው የላቀ የግዳጅና የሥራ አፈጻጸም ስኬት በድሬዳዋ ከተማ በሚገኘው የምድቡ ጠቅላይ መምሪያ የእውቅናና የምስጋና መርሐ ግብር ተካሂዷል፡፡
ሌተናል ጄኔራል ይልማ መርዳሳ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፥ መከላከያ ሠራዊት በሰው ኃይልና በቴክኖሎጂ ከፍተኛ ለውጥ እያደረገ ይገኛል፡፡
አሁን የምንገኝበት ዘመን የውጊያ አካሄድና ስልት ለመገመት በሚያዳግት መልኩ በፍጥነት እየተቀያየረ ነው ያሉት አዛዡ፥ ኢትዮጵያ በምትገኝበት ቀጣናም ያለው የኃይል አሰላለፍ ተለዋዋጭና ኢ-ተገማች መሆኑን ጠቁመዋል።
የኢፌዴሪ አየር ኃይልም ይህንን ታሳቢ በማድረግ የዘመኑን ቴክኖሎጂ መጠቀም የሚችል የሰው ኃይል በማብቃት፣ በርካታ ፓይለቶችን፣ ቴክኒሽያኖችንና የአስተዳደር ባለሙያዎች እያፈራ መሆኑንና የዘመኑን የውጊያ ቴክኖሎጂዎች እየታጠቀ እንደሚገኝ አረጋግጠዋል።
3ኛ አየር ምድብም የሪፎርሙ አካል በመሆን በርካታ ሥራዎችን በማከናወን ልዩ ታሪክ ያለው መሆኑንም አንስተዋል።
ምድቡ ኮሎኔል በዛብህ ጴጥሮስ እና ኮሎኔል ባጫ ሁንዴን የመሳሰሉ በርካታ ጀግኖችን ያፈራ መሆኑን አስታውሰው፥ አሁንም ያንን የጀግንነት ታሪክ እያደሰ በርካታ ተተኪ ወጣት በራሪዎችን በአጭር ጊዜ፣ በጥራትና በብዛት እያፈራ ይገኛል ነው ያሉት።
የሚለወጠውን የውጊያ አውድና የኃይል አሰላለፍ በመገንዘብ አመራሩና ሠራዊቱ ራሱን ከጊዜው ጋር ማዘመን እንዳለበት አስገንዝበዋል።
ኢትዮጵያን ሊፈታተኑ የሚሞክሩ ጠላቶችን መመከትና ድባቅ መምታት የሚያስችል ጀግና ተቋም መገንባቱን ገልጸው፥ የምድቡ አመራሮችና የሠራዊት አባላት ግዳጃቸውን በጀግንነትና በስኬት በመወጣታቸው ሊኮሩ ይገባል ብለዋል፡፡
በቀጣይም ታላላቅ ተልዕኮዎች እንደሚጠበቁ በመረዳት በሁሉም ረገድ ዝግጁነትን ማጠናከር እንደሚያስፈልግ ገልፀዋል።
Seledadotio
Seledadotio
5 days ago
ዜና እረፍት | ሲስተር ብርቅነሽ ከበደ – የምሕረት፣ የጀግንነትና የአገር አገልግሎት ተምሳሌት አረፈች
#ethiopia | የኢትዮጵያ የመጀመሪያዎቹ ፕሮፌሽናል ነርሶች መካከል አንዷ፣ የኮሪያ ጦርነት ዘማች፣ የቀይ መስቀል በጎ ፈቃደኛ እና ዓለም አቀፍ የነርስነት ክብር ተሸላሚ የነበሩት መቶ አለቃ ሲስተር ብርቅነሽ ከበደ በ96 ዓመታቸው አርፈዋል።
ሲስተር ብርቅነሽ በአዲስ አበባ ከአቶ ከበደ ዘውገ እና ከወ/ሮ አልመዝ የግሉ ተወለዱ። ወላጆቻቸውን በለጋ ዕድሜያቸው በሞት ካጡ በኋላ፣ በአያታቸው ወ/ሮ ላቀች ጻታ እጅ አደጉ። የአባታቸው የአርበኝነት ታሪክ በመታሰቡ፣ በእቴጌ መነን የሴቶች አዳሪ ትምህርት ቤት በነጻ እንዲማሩ እድል አግኝተዋል።
በኋላም በወቅቱ ቀዳማዊ ኃይለሥላሴ ሆስፒታል (አሁን የካቲት 12 መታሰቢያ ሆስፒታል) በነበረው የኢትዮጵያ የመጀመሪያ የነርሶች ትምህርት ቤት ተምረው፣ ከሀገሪቱ የመጀመሪያዎቹ ዘጠኝ ፕሮፌሽናል ነርሶች መካከል በክብር ተመርቀዋል።
በ1943 ዓ.ም. ከሦስተኛው ቃኘው ሻለቃ ጋር ወደ ኮሪያ በማቅናት፣ ከሁለት ጥቁር አፍሪካዊ ሴት ነርሶች አንዷ ሆነው ታሪክ ሠርተዋል። ከሲስተር አስቴር አያና ጋር በመሆን የኢትዮጵያ የመጀመሪያዎቹ የቀይ መስቀል ዘማቾች በመሆን በተባበሩት መንግሥታት ሥር በኮሪያ ጦርነት ውስጥ ለወታደሮች ሕክምና እና ሰብዓዊ አገልግሎት ሰጥተዋል። ከሕክምና ሥራቸው በተጨማሪ ለኢትዮጵያውያን ወታደሮች የትርጉም አገልግሎትም አበርክተዋል።
ከኮሪያ በኋላ በጃፓን ወታደራዊ ሆስፒታል እንዲሁም በኢትዮጵያ በክብር ዘበኛ ሆስፒታል፣ በጳውሎስ ሆስፒታል፣ በድሬዳዋና በአዲስ አበባ በሚገኙ የጤና ተቋማት ለብዙ ዓመታት በታማኝነት አገልግለዋል።
ለሰብዓዊ አገልግሎታቸው ዓለም አቀፍ ዕውቅና በማግኘት፣ በነርስነት ሙያ ከፍተኛ ክብር የሆነውን Florence Nightingale Award የተሸለሙ ጥቂት አፍሪካውያን ሴቶች መካከል አንዷ ሆነዋል።
የአገር አገልግሎታቸውን ለማክበር፣ እናት ባንክ በቦሌ ቡልቡላ የሚገኘውን አንድ ቅርንጫፍ በስማቸው ሰይሟል፤ ይህም ለሀገር ያበረከቱትን የማይረሳ አስተዋፅኦ የሚያሳይ የክብር ምልክት ነው።
መቶ አለቃ ሲስተር ብርቅነሽ ከበደ ሐምሌ 23 ቀን 2018 ዓ.ም. በ96 ዓመታቸው አርፈዋል። ከባለቤታቸው ከጄኔራል ደስታ ገመዳ ጋር ያፈሯቸውን አራት ልጆችና ስምንት የልጅ ልጆች ትተው አልፈዋል።
ሲስተር ብርቅነሽ ከበደ በጀግንነታቸው፣ በሰብዓዊነታቸው እና ለሀገራቸው ባበረከቱት አገልግሎት በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ ለዘላለም የሚታወሱ ባለውለታ ሆነው ይኖራሉ።
ነፍሳቸውን በሰላም ያሳርፍ።
#tizbit Assefa
#ethiopia | የኢትዮጵያ የመጀመሪያዎቹ ፕሮፌሽናል ነርሶች መካከል አንዷ፣ የኮሪያ ጦርነት ዘማች፣ የቀይ መስቀል በጎ ፈቃደኛ እና ዓለም አቀፍ የነርስነት ክብር ተሸላሚ የነበሩት መቶ አለቃ ሲስተር ብርቅነሽ ከበደ በ96 ዓመታቸው አርፈዋል።
ሲስተር ብርቅነሽ በአዲስ አበባ ከአቶ ከበደ ዘውገ እና ከወ/ሮ አልመዝ የግሉ ተወለዱ። ወላጆቻቸውን በለጋ ዕድሜያቸው በሞት ካጡ በኋላ፣ በአያታቸው ወ/ሮ ላቀች ጻታ እጅ አደጉ። የአባታቸው የአርበኝነት ታሪክ በመታሰቡ፣ በእቴጌ መነን የሴቶች አዳሪ ትምህርት ቤት በነጻ እንዲማሩ እድል አግኝተዋል።
በኋላም በወቅቱ ቀዳማዊ ኃይለሥላሴ ሆስፒታል (አሁን የካቲት 12 መታሰቢያ ሆስፒታል) በነበረው የኢትዮጵያ የመጀመሪያ የነርሶች ትምህርት ቤት ተምረው፣ ከሀገሪቱ የመጀመሪያዎቹ ዘጠኝ ፕሮፌሽናል ነርሶች መካከል በክብር ተመርቀዋል።
በ1943 ዓ.ም. ከሦስተኛው ቃኘው ሻለቃ ጋር ወደ ኮሪያ በማቅናት፣ ከሁለት ጥቁር አፍሪካዊ ሴት ነርሶች አንዷ ሆነው ታሪክ ሠርተዋል። ከሲስተር አስቴር አያና ጋር በመሆን የኢትዮጵያ የመጀመሪያዎቹ የቀይ መስቀል ዘማቾች በመሆን በተባበሩት መንግሥታት ሥር በኮሪያ ጦርነት ውስጥ ለወታደሮች ሕክምና እና ሰብዓዊ አገልግሎት ሰጥተዋል። ከሕክምና ሥራቸው በተጨማሪ ለኢትዮጵያውያን ወታደሮች የትርጉም አገልግሎትም አበርክተዋል።
ከኮሪያ በኋላ በጃፓን ወታደራዊ ሆስፒታል እንዲሁም በኢትዮጵያ በክብር ዘበኛ ሆስፒታል፣ በጳውሎስ ሆስፒታል፣ በድሬዳዋና በአዲስ አበባ በሚገኙ የጤና ተቋማት ለብዙ ዓመታት በታማኝነት አገልግለዋል።
ለሰብዓዊ አገልግሎታቸው ዓለም አቀፍ ዕውቅና በማግኘት፣ በነርስነት ሙያ ከፍተኛ ክብር የሆነውን Florence Nightingale Award የተሸለሙ ጥቂት አፍሪካውያን ሴቶች መካከል አንዷ ሆነዋል።
የአገር አገልግሎታቸውን ለማክበር፣ እናት ባንክ በቦሌ ቡልቡላ የሚገኘውን አንድ ቅርንጫፍ በስማቸው ሰይሟል፤ ይህም ለሀገር ያበረከቱትን የማይረሳ አስተዋፅኦ የሚያሳይ የክብር ምልክት ነው።
መቶ አለቃ ሲስተር ብርቅነሽ ከበደ ሐምሌ 23 ቀን 2018 ዓ.ም. በ96 ዓመታቸው አርፈዋል። ከባለቤታቸው ከጄኔራል ደስታ ገመዳ ጋር ያፈሯቸውን አራት ልጆችና ስምንት የልጅ ልጆች ትተው አልፈዋል።
ሲስተር ብርቅነሽ ከበደ በጀግንነታቸው፣ በሰብዓዊነታቸው እና ለሀገራቸው ባበረከቱት አገልግሎት በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ ለዘላለም የሚታወሱ ባለውለታ ሆነው ይኖራሉ።
ነፍሳቸውን በሰላም ያሳርፍ።
#tizbit Assefa
7 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) በድሬዳዋ-1 ምርጫ ክልል ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በግል እጩነት ቀርበው የነበሩት ዶ/ር ሀብታሙ አለሙ በምርጫው ሂደት እና በሚመለከታቸው ተቋማት ላይ እምነት አጥቻለሁ በሚል ከምርጫው ራሳቸውን ካገለሉ በኋላ መታሰራቸው ይታወቃል። ከወር በላይ የታሰሩት ዶክተሩ ዛሬ በዋስ ከእስር መለቀቃቸውን ሰምተናል።
13 days ago
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ-ክርስቲያን የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ስራ አስኪያጅ ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ እና የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ፀሀፊ ብፅዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ የቁልቢ ገብርኤል የንግስ በዓልን ለማክበር ድሬዳዋ ከተማ ገቡ
20 days ago
“ዕድሜ ለህልም እንቅፋት አይደለም”፦ የ62 ዓመቱ አባት ከልጃቸው ጋር የ12ኛ ክፍል ፈተናን እየወሰዱ ነው
*********************
ዕድሜ ለህልም መሳካት ማነቆ ሳይሆን ለቁርጠኝነት መለኪያ መሆኑን በተግባር እያሳዩ የሚገኙት የ62 ዓመቱ አቶ ዩሱፍ ኢብራሂም፣ በዘንድሮው የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና የብዙዎችን ትኩረት ስበዋል።
ከሶማሊ ክልል ሲቲ ዞን ጎታ ቢቄ ወረዳ የመጡት አቶ ዩሱፍ፣ ከገዛ ልጃቸው ጋር በመሆን በድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ የፈተና አዳራሽ በመገኘት የዕውቀት ጉዟቸውን እያከናወኑ ይገኛሉ።
አባትና ልጅ በአንድ የፈተና ጣቢያ መፈተናቸው ለፈተናው አዳራሽ ልዩ ድምቀት የፈጠረ ሲሆን፣ አቶ ዩሱፍ ከልጆቻቸውና ከልጅ ልጆቻቸው እኩያ ከሆኑ ወጣቶች ጋር ጎን ለጎን ተቀምጠው መፈተናቸው ታላቅ ክብርና ደስታ እንደሰጣቸው ይናገራሉ።
አቶ ዩሱፍ በዚህ ዕድሜያቸው ፈተናውን ለመውሰድ የወሰኑት የራሳቸውን ህልም ለማሳካት ብቻ ሳይሆን፣ በትምህርታቸው ተስፋ ለሚቆርጡ ወጣቶች አርአያ በመሆን መነቃቃትን ለመፍጠር ጭምር ነው።
“ትምህርት የሀገር ፍቅር መገለጫ ነው” የሚሉት አቶ ዩሱፍ፣ ለግለሰብም ሆነ ለሀገር እድገት ትምህርት ዋነኛው ቁልፍ መሆኑን በጽኑ ያምናሉ። ተማሪዎች በሙሉ በትምህርታቸው በርትተው በመማር፣ ነገ አመርቂ ውጤት በማምጣት ሀገራቸውን በታማኝነት ማገልገል እንዳለባቸውም መልእክታቸውን አስተላልፈዋል።
የአቶ ዩሱፍ የዕውቀት ጉዞ በዚህ የ12ኛ ክፍል ፈተና ላይ የሚያበቃ አይደለም። ፈተናውን በከፍተኛ ውጤት በማለፍ ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋም በመግባት፣ የጀመሩትን የዕውቀት ጉዞ የመቀጠልና በዩኒቨርሲቲ የመመረቅ ትልቅ ራዕይ ሰንቀዋል።
የ62 ዓመቱ አባት ይህ ታሪካዊ ርምጃ፣ ትምህርት ለማንኛውም ዕድሜ የሰው ልጅ የላቀ መዳረሻ መሆኑን በተግባር እያረጋገጠ ይገኛል።
በቴዎድሮስ ታደሰ
#ኢትዮጵያ #ኢትዮጵያትማር #ethiopia #education
*********************
ዕድሜ ለህልም መሳካት ማነቆ ሳይሆን ለቁርጠኝነት መለኪያ መሆኑን በተግባር እያሳዩ የሚገኙት የ62 ዓመቱ አቶ ዩሱፍ ኢብራሂም፣ በዘንድሮው የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና የብዙዎችን ትኩረት ስበዋል።
ከሶማሊ ክልል ሲቲ ዞን ጎታ ቢቄ ወረዳ የመጡት አቶ ዩሱፍ፣ ከገዛ ልጃቸው ጋር በመሆን በድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ የፈተና አዳራሽ በመገኘት የዕውቀት ጉዟቸውን እያከናወኑ ይገኛሉ።
አባትና ልጅ በአንድ የፈተና ጣቢያ መፈተናቸው ለፈተናው አዳራሽ ልዩ ድምቀት የፈጠረ ሲሆን፣ አቶ ዩሱፍ ከልጆቻቸውና ከልጅ ልጆቻቸው እኩያ ከሆኑ ወጣቶች ጋር ጎን ለጎን ተቀምጠው መፈተናቸው ታላቅ ክብርና ደስታ እንደሰጣቸው ይናገራሉ።
አቶ ዩሱፍ በዚህ ዕድሜያቸው ፈተናውን ለመውሰድ የወሰኑት የራሳቸውን ህልም ለማሳካት ብቻ ሳይሆን፣ በትምህርታቸው ተስፋ ለሚቆርጡ ወጣቶች አርአያ በመሆን መነቃቃትን ለመፍጠር ጭምር ነው።
“ትምህርት የሀገር ፍቅር መገለጫ ነው” የሚሉት አቶ ዩሱፍ፣ ለግለሰብም ሆነ ለሀገር እድገት ትምህርት ዋነኛው ቁልፍ መሆኑን በጽኑ ያምናሉ። ተማሪዎች በሙሉ በትምህርታቸው በርትተው በመማር፣ ነገ አመርቂ ውጤት በማምጣት ሀገራቸውን በታማኝነት ማገልገል እንዳለባቸውም መልእክታቸውን አስተላልፈዋል።
የአቶ ዩሱፍ የዕውቀት ጉዞ በዚህ የ12ኛ ክፍል ፈተና ላይ የሚያበቃ አይደለም። ፈተናውን በከፍተኛ ውጤት በማለፍ ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋም በመግባት፣ የጀመሩትን የዕውቀት ጉዞ የመቀጠልና በዩኒቨርሲቲ የመመረቅ ትልቅ ራዕይ ሰንቀዋል።
የ62 ዓመቱ አባት ይህ ታሪካዊ ርምጃ፣ ትምህርት ለማንኛውም ዕድሜ የሰው ልጅ የላቀ መዳረሻ መሆኑን በተግባር እያረጋገጠ ይገኛል።
በቴዎድሮስ ታደሰ
#ኢትዮጵያ #ኢትዮጵያትማር #ethiopia #education
Sponsored by
Surafel
22 days ago
በሕዝብ የባለቤትነት መንፈስ ዋዜማው ላይ የደረሰው የሀገራዊ ምክክር ጉባኤ
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 7፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የሀገራዊ ምክክር ጉባኤ የሚካሄድበት ዋዜማ ላይ እንገኛለን። እዚህ ለመድረስ ባለፉት አራት ዓመታት ከቅድመ ዝግጅት ምዕራፍ ጀምሮ ብዙ ተሰርቷል።
ሀገራዊ ምክክር ጉባኤው በስምንት የተለዩ አጀንዳዎች ላይ ከነገ ጀምሮ ለመምከር ዝግጅት ተጠናቅቋል። በምክክር ጉባኤው ላይ የሚሳተፉ ከ4 ሺህ በላይ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ተወካዮች አዲስ አበባ ከትመዋል።
የጉባኤው ተሳታፊዎች መልክ ኢትዮጵያን የሚመስልና ሁሉም ኢትዮጵያዊ የተወከለበት እንዲሆን በጥንቃቄ ተሰርቷል።
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በምክክር ጉባዔ ወቅት ሙያዊ ማብራሪያን ጨምሮ የተለያዩ ድጋፍ የሚያደርጉ ሰዎችን ዝግጁ አድርጓል።
የኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር መስፍን አርዓያ (ፕ/ር) እንደሚሉት÷ በሀገራዊ ምክክር ሒደት ለዘመናት ሲንከባለሉ የመጡ አለመግባባቶችን በሰለጠነ መንገድ ለመፍታትና ሀገራዊ መግባባት ለመፍጠር የሚያስችል ምሕዳር ተፈጥሯል፡፡
ላለፉት አራት ዓመታት ሰፊ ዝግጅት ተደርጓል፤ በዚህም በተለያዩ ምዕራፎች ዋናውን ሀገራዊ የምክክር ጉባዔ ማካሄድ የሚያስችል አሳታፊና አካታች የአጀንዳ ማሰባሰብና ተሳታፊ ልየታ ሥራ ተከናውኗል።
ከተደረጉት ዝግጅቶች መካከል በጉባኤው ወቅት ማብራሪያ ለሚያስፈልጋቸው ጉዳዮች ማብራሪያ የሚሰጡ ልሂቃን ማዘጋጀት አንዱ ነው።
ልሒቃኑ በምክክሩ ሒደት የጋራ መረዳት እንዲፈጠር፣ ውስብስብ ጉዳዮችን ታሪካዊ አመጣጥና የታዩ ክስተቶችን በጥናት አስደግፎ በማመላከት ወደ መፍትሄ ማድረስ ይጠበቅባቸዋል።
ወደ ምክክር ጉባኤ የሚያደርሱ መሰረታዊ ተግባራት ሲያከናውን የቆየው የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን፤ ሂደቱ አካታች፣ አሳታፊ እና ተዓማኒ እንዲሆን በተደረገው ጥረት በመላው ሀገሪቱ ከሚገኙ ወረዳዎች መካከል 1 ሺህ 234ቱን ማሳተፍ ተችሏል
ይህም 93 በመቶ የሚሸፍን መሆኑ የተደራሽነት አድማሱን የላቀ አድርጎታል።
የፌደራል ባለድርሻ አካላት፣ አዲስ አበባ እና ድሬዳዋ ከተማ አስተዳደሮችን ጨምሮ በ12 ክልሎች ሰፊ እና ስኬታማ የአጀንዳ ማሰባሰብ ተግባር ተከናውኗል።
በውጭ ሀገር የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያንም እንዲሳተፉ መደረጉ ከተለያዩ አቅጣጫዎች የሚነሱ ጥያቄዎችን የሚመልስ ያደርገዋል።
አጀንዳ የተሰባሰበባቸው አካባቢዎች ለዋናው ጉባኤ የሚወክላቸውን ሰዎች መርጦ ልኳል።
የምክክር ሂደቱ ከጅምሩ አንስቶ ግልጽ፣ ገለልተኛ እና አሳታፊ በሆነ አሰራር እንዲመራ መደረጉ ከምክክር ሂደቱ የሚፈለገውን ውጤት ለማምጣት መንገድ የጠረገ ነው።
የኢትዮጵያ ሕዝብ ለሂደቱ የሰጠው ትኩረት እና ያሳየው የባለቤትነት መንፈስ እጅግ የሚያበረታታ ሲሆን፤ ሕዝቡ ታሪክ የማይረሳው ሀገራዊ ኃላፊነት ተወጥቷል።
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 7፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የሀገራዊ ምክክር ጉባኤ የሚካሄድበት ዋዜማ ላይ እንገኛለን። እዚህ ለመድረስ ባለፉት አራት ዓመታት ከቅድመ ዝግጅት ምዕራፍ ጀምሮ ብዙ ተሰርቷል።
ሀገራዊ ምክክር ጉባኤው በስምንት የተለዩ አጀንዳዎች ላይ ከነገ ጀምሮ ለመምከር ዝግጅት ተጠናቅቋል። በምክክር ጉባኤው ላይ የሚሳተፉ ከ4 ሺህ በላይ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ተወካዮች አዲስ አበባ ከትመዋል።
የጉባኤው ተሳታፊዎች መልክ ኢትዮጵያን የሚመስልና ሁሉም ኢትዮጵያዊ የተወከለበት እንዲሆን በጥንቃቄ ተሰርቷል።
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በምክክር ጉባዔ ወቅት ሙያዊ ማብራሪያን ጨምሮ የተለያዩ ድጋፍ የሚያደርጉ ሰዎችን ዝግጁ አድርጓል።
የኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር መስፍን አርዓያ (ፕ/ር) እንደሚሉት÷ በሀገራዊ ምክክር ሒደት ለዘመናት ሲንከባለሉ የመጡ አለመግባባቶችን በሰለጠነ መንገድ ለመፍታትና ሀገራዊ መግባባት ለመፍጠር የሚያስችል ምሕዳር ተፈጥሯል፡፡
ላለፉት አራት ዓመታት ሰፊ ዝግጅት ተደርጓል፤ በዚህም በተለያዩ ምዕራፎች ዋናውን ሀገራዊ የምክክር ጉባዔ ማካሄድ የሚያስችል አሳታፊና አካታች የአጀንዳ ማሰባሰብና ተሳታፊ ልየታ ሥራ ተከናውኗል።
ከተደረጉት ዝግጅቶች መካከል በጉባኤው ወቅት ማብራሪያ ለሚያስፈልጋቸው ጉዳዮች ማብራሪያ የሚሰጡ ልሂቃን ማዘጋጀት አንዱ ነው።
ልሒቃኑ በምክክሩ ሒደት የጋራ መረዳት እንዲፈጠር፣ ውስብስብ ጉዳዮችን ታሪካዊ አመጣጥና የታዩ ክስተቶችን በጥናት አስደግፎ በማመላከት ወደ መፍትሄ ማድረስ ይጠበቅባቸዋል።
ወደ ምክክር ጉባኤ የሚያደርሱ መሰረታዊ ተግባራት ሲያከናውን የቆየው የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን፤ ሂደቱ አካታች፣ አሳታፊ እና ተዓማኒ እንዲሆን በተደረገው ጥረት በመላው ሀገሪቱ ከሚገኙ ወረዳዎች መካከል 1 ሺህ 234ቱን ማሳተፍ ተችሏል
ይህም 93 በመቶ የሚሸፍን መሆኑ የተደራሽነት አድማሱን የላቀ አድርጎታል።
የፌደራል ባለድርሻ አካላት፣ አዲስ አበባ እና ድሬዳዋ ከተማ አስተዳደሮችን ጨምሮ በ12 ክልሎች ሰፊ እና ስኬታማ የአጀንዳ ማሰባሰብ ተግባር ተከናውኗል።
በውጭ ሀገር የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያንም እንዲሳተፉ መደረጉ ከተለያዩ አቅጣጫዎች የሚነሱ ጥያቄዎችን የሚመልስ ያደርገዋል።
አጀንዳ የተሰባሰበባቸው አካባቢዎች ለዋናው ጉባኤ የሚወክላቸውን ሰዎች መርጦ ልኳል።
የምክክር ሂደቱ ከጅምሩ አንስቶ ግልጽ፣ ገለልተኛ እና አሳታፊ በሆነ አሰራር እንዲመራ መደረጉ ከምክክር ሂደቱ የሚፈለገውን ውጤት ለማምጣት መንገድ የጠረገ ነው።
የኢትዮጵያ ሕዝብ ለሂደቱ የሰጠው ትኩረት እና ያሳየው የባለቤትነት መንፈስ እጅግ የሚያበረታታ ሲሆን፤ ሕዝቡ ታሪክ የማይረሳው ሀገራዊ ኃላፊነት ተወጥቷል።
23 days ago
u12e8u1218u1300u1218u122au12eb u12f0u130du121eu121d u1235u12acu1273u121b ..u12e8u12f5u122cu12f3u12cb u1290u1343 u1295u130du12f5 u1240u1320u1293 #u1356u12f5u12abu1235u1275 #u134bu1293u1356u12f5u12abu1235u1275 #u1309u1265u129du1275 #u134bu1293u121au12f2u12ebu12aeu122du1356u122cu123du1295 #fanapodcast #fanadigitalmedia #fanamediacorporation #poodkaastiifaanaa #u0641u0627u0646u0627_u0639u0631u0628u064a_u0628u0648u062fu0643u0627u0633u062a ","delight_ranges":[],"image_ranges":[],"inline_style_ranges":[],"aggregated_ranges":[],"ranges":[{"entity":{"__typename":"Hashtag","__isEntity":"Hashtag","url":"https://www.facebook.com/h...
የመጀመሪያ ደግሞም ስኬታማ ..የድሬዳዋ ነፃ ንግድ ቀጠና #ፖድካስት #ፋናፖድካስት #ጉብኝት #ፋናሚዲያኮርፖሬሽን #fanapodcast #fanadigitalmedia #fanamediacorporation #poodkaastiifaanaa #فانا_عربي_بودكاست
23 days ago
u12e8u1218u1300u1218u122au12eb u12f0u130du121eu121d u1235u12acu1273u121b ..u12e8u12f5u122cu12f3u12cb u1290u1343 u1295u130du12f5 u1240u1323u1293
u12dbu122c u121du123du1275 2u136100 u1260u134bu1293 u1356u12f5u12abu1235u1275 u12edu1320u1265u1241u1295!
#u1309u1265u129du1275 #u1356u12f5u12abu1235u1275 #u134bu1293u1356u12f5u12abu1235u1275 #u134bu1293u121au12f2u12ebu12aeu122du1356u122cu123du1295 #fanapodcast #fanadigitalmedia #fanamediacorporation #poodkaastiifaanaa #fanadigitalmedia #u0641u0627u0646 ","delight_ranges":[],"image_ranges":[],"inline_style_ranges":[],"aggregated_ranges":[],"ranges":[{"entity":{"__typename":"Hashtag","__isEntity":"Hashtag","url":"https://www.facebook.com/h...
የመጀመሪያ ደግሞም ስኬታማ ..የድሬዳዋ ነፃ ንግድ ቀጣና
ዛሬ ምሽት 2፡00 በፋና ፖድካስት ይጠብቁን!
#ጉብኝት #ፖድካስት #ፋናፖድካስት #ፋናሚዲያኮርፖሬሽን #fanapodcast #fanadigitalmedia #fanamediacorporation #poodkaastiifaanaa #fanadigitalmedia #فان
23 days ago
ግልግል
ግብር በቴሌብር!
ሰነድ ማዘጋጀትና ሰልፍ መሰለፍ ቀረ፤ የዓመቱን ግብር በቴሌብር አሁኑኑ እንክፈል!
የገቢዎች ሚኒስቴርን፣ የአዲስ አበባ (ከፍተኛ፣ መካከለኛና አነስተኛ)፣ የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደርን እንዲሁም የኦሮሚያ፣ የአማራ፣ የሲዳማ፣ የደቡብ ኢትዮጵያ፣ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ፣ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦችን፣ የሱማሌ፣ የሐረሪ፣ የአፋር እና የቤንሻንጉል ጉሙዝ ገቢዎች የግብር ክፍያ በአስተማማኝ ሁኔታ አሁኑኑ በቴሌብር ይክፈሉ!
ቴሌብር ሱፐርአፕን https://bit.ly/telebirr_Su... ጭነን ስንከፍል እንዲህ ነን!
#ደንበኛ_ስንሆን_እንዲህ_ነን #ስንመዘገብ_እንዲህ_ነን #ስንጭን_እንዲህ_ነን #ስናስጀምር_እንዲህ_ነን
ግብር በቴሌብር!
ሰነድ ማዘጋጀትና ሰልፍ መሰለፍ ቀረ፤ የዓመቱን ግብር በቴሌብር አሁኑኑ እንክፈል!
የገቢዎች ሚኒስቴርን፣ የአዲስ አበባ (ከፍተኛ፣ መካከለኛና አነስተኛ)፣ የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደርን እንዲሁም የኦሮሚያ፣ የአማራ፣ የሲዳማ፣ የደቡብ ኢትዮጵያ፣ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ፣ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦችን፣ የሱማሌ፣ የሐረሪ፣ የአፋር እና የቤንሻንጉል ጉሙዝ ገቢዎች የግብር ክፍያ በአስተማማኝ ሁኔታ አሁኑኑ በቴሌብር ይክፈሉ!
ቴሌብር ሱፐርአፕን https://bit.ly/telebirr_Su... ጭነን ስንከፍል እንዲህ ነን!
#ደንበኛ_ስንሆን_እንዲህ_ነን #ስንመዘገብ_እንዲህ_ነን #ስንጭን_እንዲህ_ነን #ስናስጀምር_እንዲህ_ነን
26 days ago
የእርዳታ ተማጽኖ
26 ዓመቱ ወጣት ሰዒድ መሐመድ ሁሴን የእኛን ድጋፍ ይፈልጋል
#ethiopia | የድሬዳዋ ከተማ ነዋሪ የሆነው የ26 ዓመቱ ወጣት ሰዒድ መሐመድ ሁሴን ሁለቱም ኩላሊቶቹ ከሥራ ውጭ በመሆናቸው ላለፉት 4 ዓመታት በከባድ ሕመም ሲሰቃይ ቆይቷል። በዚህ ጊዜም የኩላሊት እጥበት (ዳያሊሲስ) ሕክምና እያደረገ ቆይቷል።
በሐኪሞች ቦርድ ውሳኔ መሠረት በአስቸኳይ ወደ ሕንድ በመጓዝ የኩላሊት ንቅለ ተከላ ሕክምና ማድረግ እንዳለበት ተገልጿል። ሆኖም ለሕክምናው የሚያስፈልገው ወጪ ከፍተኛ በመሆኑ የአቅም ችግር ገጥሞታል።
ስለዚህ በሀገር ውስጥና በውጭ የምትገኙ ኢትዮጵያውያንና ኤርትራውያን ወገኖች በአቅማችሁ መጠን የገንዘብ ድጋፍ በማድረግ ይህን ወጣት ሕይወቱን እንዲያተርፍ እንድትረዱት በክብር እንጠይቃለን።
የድጋፍ መረጃ
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ (CBE)
የአካውንት ቁጥር: 1000290802467
የአካውንቱ ስም: ሰዒድ መሐመድ ሁሴን
ኢ-ብር / ቴሌብር
ስልክ ቁጥር: 0935 284 117
ስም: ሰዒድ መሐመድ
አንድ ትንሽ ድጋፍዎ ለአንድ ወጣት አዲስ የሕይወት ተስፋ ሊሆን ይችላል።
🙏 እባክዎ መልእክቱን በማጋራትም ቢሆን የበኩልዎን አስተዋጽኦ ያድርጉ። #ሼር #share
26 ዓመቱ ወጣት ሰዒድ መሐመድ ሁሴን የእኛን ድጋፍ ይፈልጋል
#ethiopia | የድሬዳዋ ከተማ ነዋሪ የሆነው የ26 ዓመቱ ወጣት ሰዒድ መሐመድ ሁሴን ሁለቱም ኩላሊቶቹ ከሥራ ውጭ በመሆናቸው ላለፉት 4 ዓመታት በከባድ ሕመም ሲሰቃይ ቆይቷል። በዚህ ጊዜም የኩላሊት እጥበት (ዳያሊሲስ) ሕክምና እያደረገ ቆይቷል።
በሐኪሞች ቦርድ ውሳኔ መሠረት በአስቸኳይ ወደ ሕንድ በመጓዝ የኩላሊት ንቅለ ተከላ ሕክምና ማድረግ እንዳለበት ተገልጿል። ሆኖም ለሕክምናው የሚያስፈልገው ወጪ ከፍተኛ በመሆኑ የአቅም ችግር ገጥሞታል።
ስለዚህ በሀገር ውስጥና በውጭ የምትገኙ ኢትዮጵያውያንና ኤርትራውያን ወገኖች በአቅማችሁ መጠን የገንዘብ ድጋፍ በማድረግ ይህን ወጣት ሕይወቱን እንዲያተርፍ እንድትረዱት በክብር እንጠይቃለን።
የድጋፍ መረጃ
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ (CBE)
የአካውንት ቁጥር: 1000290802467
የአካውንቱ ስም: ሰዒድ መሐመድ ሁሴን
ኢ-ብር / ቴሌብር
ስልክ ቁጥር: 0935 284 117
ስም: ሰዒድ መሐመድ
አንድ ትንሽ ድጋፍዎ ለአንድ ወጣት አዲስ የሕይወት ተስፋ ሊሆን ይችላል።
🙏 እባክዎ መልእክቱን በማጋራትም ቢሆን የበኩልዎን አስተዋጽኦ ያድርጉ። #ሼር #share
27 days ago
በድሬዳዋ ከተማ 548 የጋራ መኖሪያ ቤቶች ዕጣ ሊወጣ ነው
#ethiopia | የድሬዳዋ አስተዳደር በኢንዱስትሪ መንደር ሳይት ሶስት የገነባቸውን የጋራ መኖሪያ ቤቶች የባለቤትነት ዕጣ ሐምሌ 4 ቀን 2018 ዓ.ም በይፋ እንደሚያወጣ አስታወቀ።
የድሬዳዋ ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ኢማጅ አብደላ በዛሬው እለት በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ እንደገለጹት፣ በዕለቱ ለዕጣ የሚቀርቡት በአጠቃላይ 548 ቤቶች ሲሆኑ፣ መስፈርቱን አሟልተው የቆጠቡ ከ7,000 በላይ ቆጣቢዎች በሂደቱ ይሳተፋሉ ብለዋል።
የከተማ አስተዳደሩ የዕጣ አወጣጡን ሂደት ሙሉ በሙሉ ግልጽና ተአማኒ ለማድረግ፣ ከሰው ንክኪ ነፃ በሆነ ዘመናዊ የቴክኖሎጂ አፕሊኬሽን እንደሚጠቀም አስታውቋል።
ዕጣው አወጣጥ ሂደትም ለሴቶች 30 በመቶ፣ ለመንግስት ሠራተኞች 20 በመቶ እንዲሁም ለአካል ጉዳተኞች 2 በመቶ ቅድሚያ የሚሰጥበት አሠራር መዘርጋቱ ተጠቁሟል።
የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር በ2019 ዓ.ም. አራት ነጥብ አምስት ሄክታር መሬት ላይ "ሳይት አራት" የተሰኘ ዘመናዊ የጋራ መኖሪያ ቤት ግንባታ ፕሮጀክት ለመጀመር ቅድመ ዝግጅቱን ማጠናቀቁን አቶ ኢማጅ አክለው ገልጸዋል።
#ድሬዳዋ #የጋራመኖሪያቤት #የቤትዕጣ #ኢትዮጵያ #ልማት #diredawa #ethiopia #housingdevelopment
#ethiopia | የድሬዳዋ አስተዳደር በኢንዱስትሪ መንደር ሳይት ሶስት የገነባቸውን የጋራ መኖሪያ ቤቶች የባለቤትነት ዕጣ ሐምሌ 4 ቀን 2018 ዓ.ም በይፋ እንደሚያወጣ አስታወቀ።
የድሬዳዋ ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ኢማጅ አብደላ በዛሬው እለት በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ እንደገለጹት፣ በዕለቱ ለዕጣ የሚቀርቡት በአጠቃላይ 548 ቤቶች ሲሆኑ፣ መስፈርቱን አሟልተው የቆጠቡ ከ7,000 በላይ ቆጣቢዎች በሂደቱ ይሳተፋሉ ብለዋል።
የከተማ አስተዳደሩ የዕጣ አወጣጡን ሂደት ሙሉ በሙሉ ግልጽና ተአማኒ ለማድረግ፣ ከሰው ንክኪ ነፃ በሆነ ዘመናዊ የቴክኖሎጂ አፕሊኬሽን እንደሚጠቀም አስታውቋል።
ዕጣው አወጣጥ ሂደትም ለሴቶች 30 በመቶ፣ ለመንግስት ሠራተኞች 20 በመቶ እንዲሁም ለአካል ጉዳተኞች 2 በመቶ ቅድሚያ የሚሰጥበት አሠራር መዘርጋቱ ተጠቁሟል።
የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር በ2019 ዓ.ም. አራት ነጥብ አምስት ሄክታር መሬት ላይ "ሳይት አራት" የተሰኘ ዘመናዊ የጋራ መኖሪያ ቤት ግንባታ ፕሮጀክት ለመጀመር ቅድመ ዝግጅቱን ማጠናቀቁን አቶ ኢማጅ አክለው ገልጸዋል።
#ድሬዳዋ #የጋራመኖሪያቤት #የቤትዕጣ #ኢትዮጵያ #ልማት #diredawa #ethiopia #housingdevelopment
Sponsored by
Surafel
27 days ago
ሰላም፤ እንደምን አደራችሁ?
የሀሳብ ልዩነቶቻችን በመነጋገርና በመደማመጥ የምንፈታቸው፣ ማንነቶቻችን ደግሞ ተቻችለን የምንኖርባቸው እንጂ በምንም መልኩ የስጋት ምንጮቻችን ሊሆኑ አይገባም።
ልዩነቶቻችንን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት ብቸኛውና አስተማማኙ መንገድ ምክክር ነው።
ምክክር የተለያዩ አመለካከቶች በነፃነት ቀርበው የሚስተናገዱበት መድረክ ከመሆኑ ባሻገር፣ ለዘላቂ ሰላም መረጋገጥ እና በማህበረሰቡ መካከል ጠንካራ የመተማመን ስሜትን ለመፍጠር ወሳኝ ሚና አለው።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባደረጉት ማብራሪያ ላይ እንዳመለከቱት፤ አሁን ላይ “እንመካከር፣ እንወያይ፣ እንፍታ” እየተባለ ያለው ችግር የአሁኑ ትውልድ የፈጠረው አይደለም፤ እኛ ባንፈጥራቸውም እንኳ አሁን ላይ በእኛ ትውልድ ላይ የወደቁትን ታሪካዊና መዋቅራዊ ችግሮች ግን በውይይት የመፍታት የጋራ ኃላፊነት አለብን።
እኛ ያላዋጣንባቸውና ያልመሰረትናቸው ችግሮች ቢሆኑም እንኳ፣ በሕዝቦች መካከል መግባባትን ለመፍጠር፣ መተማመንን ለማስፈንና ለኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላም ሲባል ተወያይቶ የመፍታት የግድ ይላል።
በጠመንጃ ኃይል እንታገላለን፣ ለሕዝባችን መብት እንቆማለን ብለው የሚያምኑ ኃይሎች በተግባር ግን መልሰው ለማህበረሰቡ ትልቅ የስጋት ምንጭ እየሆኑ መምጣታቸውን እያየን ነው።
ይህ ዓይነቱ አካሄድ ወጣቶችን ከትምህርት ገበታቸው ያለያያል፣ ጦርነትና ለጥፋት ያመጣል፣ ሀገርንና ማህበረሰብን ለኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ቀውስ ይዳርጋል።
በመሆኑም በጦርነትና በኃይል ፍላጎትን ለመጫን መሞከር ትውልድን ከማጥፋት ባለፈ መፍትሄ ሊያመጣ እንደማይችል በተግባር የታየ እውነት ነው።
ማንኛውም ዜጋ በነፃነት የመኖር፣ የመማር እና የመስራት መብቱ እንዲከበር የኢትዮጵያን ሰላም በጋራ ማስጠበቅ ይኖርብናል።
ለልጆቻችን የተሻለች፣ የበለጸገችና የተረጋጋች ሀገር ለማውረስ ስንል የመወያየትና የመደማመጥ ኃላፊነታችንን መወጣት ይጠበቅብናል።
በአሁኑ ወቅት ኢትዮጵያ የሚመክሩላትን፣ የሚወያዩላትንና መፍትሄ የሚያፈልቁላትን ልጆቿን ለመቀበል ተሰናድታለች።
ሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም በሚካሄደዉ ሀገራዊ የምክክር ጉባዔ የሚሳተፉ ከ4 ሺህ ተወካዮች በአዲስ አበባ እየተሰባሰቡ ነው፡፡
ተወካዮቹ በክልሎች፣ ከተማ አስተዳደሮች፣ በፌዴራል ደረጃ እንዲሁም በዳያስፖራው የአጀንዳ ማሰባሰብ ሒደት በሀገራዊ ምክክር ጉባዔው ላይ እንዲሳተፉ የተመረጡ ወኪሎች ናቸው፡፡
በምክክር ጉባዔው ላይ በሰከነ እና መደማመጥ በተሞላበት ስሜት የልዩነት ምንጭ የሆኑ ችግሮችን ለመፍታት ዝግጁ የሆኑት ተወካዮቹ፤ ለምክክር ጉባዔው ስኬት ከፍተኛ ኃላፊነት ተጥሎባቸዋል።
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ለዋናው ሀገራዊ ጉባዔ ስምንት ዋና ዋና አጀንዳዎችን ለሕዝብ ይፋ ማድረጉ ይታወቃል።
እነዚህም ፡-
👉 የሀገር ግንባታ
👉 የመንግሥት አደረጃጀትና ቅርጽ፣ የፖለቲካ ሥርዓት፣ የፖለቲካ ውክልና እና የምርጫ ሥርዓት፣
👉 የፌዴራል ከተሞች አዲስ አበባና ድሬዳዋ ጉዳይ፣
👉 የሃይማኖት ጉዳዮች፣ታሪካዊ ቅሬታዎች እና እርቅ
👉 የተቋማት ግንባታ፣ የሕግ የበላይነትና ሰብዓዊ መብቶች፣
👉 ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንዲሁም የአርሶ አደሮች እና አርብቶ አደሮች ጉዳዮች
👉 ሙስና እና መልካም አስተዳደር እና
👉 የሰላም ግንባታ ናቸው፡፡
የሀሳብ ልዩነቶቻችን በመነጋገርና በመደማመጥ የምንፈታቸው፣ ማንነቶቻችን ደግሞ ተቻችለን የምንኖርባቸው እንጂ በምንም መልኩ የስጋት ምንጮቻችን ሊሆኑ አይገባም።
ልዩነቶቻችንን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት ብቸኛውና አስተማማኙ መንገድ ምክክር ነው።
ምክክር የተለያዩ አመለካከቶች በነፃነት ቀርበው የሚስተናገዱበት መድረክ ከመሆኑ ባሻገር፣ ለዘላቂ ሰላም መረጋገጥ እና በማህበረሰቡ መካከል ጠንካራ የመተማመን ስሜትን ለመፍጠር ወሳኝ ሚና አለው።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባደረጉት ማብራሪያ ላይ እንዳመለከቱት፤ አሁን ላይ “እንመካከር፣ እንወያይ፣ እንፍታ” እየተባለ ያለው ችግር የአሁኑ ትውልድ የፈጠረው አይደለም፤ እኛ ባንፈጥራቸውም እንኳ አሁን ላይ በእኛ ትውልድ ላይ የወደቁትን ታሪካዊና መዋቅራዊ ችግሮች ግን በውይይት የመፍታት የጋራ ኃላፊነት አለብን።
እኛ ያላዋጣንባቸውና ያልመሰረትናቸው ችግሮች ቢሆኑም እንኳ፣ በሕዝቦች መካከል መግባባትን ለመፍጠር፣ መተማመንን ለማስፈንና ለኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላም ሲባል ተወያይቶ የመፍታት የግድ ይላል።
በጠመንጃ ኃይል እንታገላለን፣ ለሕዝባችን መብት እንቆማለን ብለው የሚያምኑ ኃይሎች በተግባር ግን መልሰው ለማህበረሰቡ ትልቅ የስጋት ምንጭ እየሆኑ መምጣታቸውን እያየን ነው።
ይህ ዓይነቱ አካሄድ ወጣቶችን ከትምህርት ገበታቸው ያለያያል፣ ጦርነትና ለጥፋት ያመጣል፣ ሀገርንና ማህበረሰብን ለኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ቀውስ ይዳርጋል።
በመሆኑም በጦርነትና በኃይል ፍላጎትን ለመጫን መሞከር ትውልድን ከማጥፋት ባለፈ መፍትሄ ሊያመጣ እንደማይችል በተግባር የታየ እውነት ነው።
ማንኛውም ዜጋ በነፃነት የመኖር፣ የመማር እና የመስራት መብቱ እንዲከበር የኢትዮጵያን ሰላም በጋራ ማስጠበቅ ይኖርብናል።
ለልጆቻችን የተሻለች፣ የበለጸገችና የተረጋጋች ሀገር ለማውረስ ስንል የመወያየትና የመደማመጥ ኃላፊነታችንን መወጣት ይጠበቅብናል።
በአሁኑ ወቅት ኢትዮጵያ የሚመክሩላትን፣ የሚወያዩላትንና መፍትሄ የሚያፈልቁላትን ልጆቿን ለመቀበል ተሰናድታለች።
ሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም በሚካሄደዉ ሀገራዊ የምክክር ጉባዔ የሚሳተፉ ከ4 ሺህ ተወካዮች በአዲስ አበባ እየተሰባሰቡ ነው፡፡
ተወካዮቹ በክልሎች፣ ከተማ አስተዳደሮች፣ በፌዴራል ደረጃ እንዲሁም በዳያስፖራው የአጀንዳ ማሰባሰብ ሒደት በሀገራዊ ምክክር ጉባዔው ላይ እንዲሳተፉ የተመረጡ ወኪሎች ናቸው፡፡
በምክክር ጉባዔው ላይ በሰከነ እና መደማመጥ በተሞላበት ስሜት የልዩነት ምንጭ የሆኑ ችግሮችን ለመፍታት ዝግጁ የሆኑት ተወካዮቹ፤ ለምክክር ጉባዔው ስኬት ከፍተኛ ኃላፊነት ተጥሎባቸዋል።
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ለዋናው ሀገራዊ ጉባዔ ስምንት ዋና ዋና አጀንዳዎችን ለሕዝብ ይፋ ማድረጉ ይታወቃል።
እነዚህም ፡-
👉 የሀገር ግንባታ
👉 የመንግሥት አደረጃጀትና ቅርጽ፣ የፖለቲካ ሥርዓት፣ የፖለቲካ ውክልና እና የምርጫ ሥርዓት፣
👉 የፌዴራል ከተሞች አዲስ አበባና ድሬዳዋ ጉዳይ፣
👉 የሃይማኖት ጉዳዮች፣ታሪካዊ ቅሬታዎች እና እርቅ
👉 የተቋማት ግንባታ፣ የሕግ የበላይነትና ሰብዓዊ መብቶች፣
👉 ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንዲሁም የአርሶ አደሮች እና አርብቶ አደሮች ጉዳዮች
👉 ሙስና እና መልካም አስተዳደር እና
👉 የሰላም ግንባታ ናቸው፡፡
29 days ago
ዋሊያዎቹ ከአምስት ዓመት በኋላ ከስደት ሊመለሱ ነው
#ethiopia | ሁለት የኢትዮጵያ ስታዲዬሞች ኢንተርናሽናል ጨዋታ እንዲያስተናግዱ የካፍን ይሁንታ አገኙ
የአፍሪካን እግር ኳስ በበላይነት የሚያስተዳድረው ካፍ ለአዲሱ የውድድርዓመት ኢንተርናሽናል ጨዋታዎችን እንዲያስተናግዱ ይሁንታ የፈቀደላቸውን ሃገራት ይፋ አድርጓል።
ኢትዬጵያም በሚያስገርም ሁኔታ ሁለት ስታዲዬሞች ኢንተርናሽናል ጨዋታ ኢንዲያስተናግዱ ፍቃድ አግኝተዋል ተብሏል።
ካፍ ይፋ ባደረገው መረጃ መሰረት የድሬዳዋ እና የአበበ ቢቂላስታዲየም ኢንተርናሽናል ጨዋታ እንዲያስተናገዱ መፈቀዱ ይነገራል።
ይህ ደግሞ ለክለቦቻችንና ለብሄራዊ ቡድኑ መልካም አጋጣሚ የሚፈጥር ከመሆኑ ባሻገር ከስደት የሚታደግ ይሆናል።
በሚቀጥለው ወር መጨረሻ ኢንተርናሽናል ጨዋታ የሚጠብቃቸው ሲዳማ ቡና እና ወልዋሎ ጨዋታቸውን በአበበ ቢቂላ ስታዲየም ለማድረግ መወሰናቸው ታውቋል።
እግር ኳስ ፌዴሬሽኑ ሁለቱን ክለቦች ጠርቶ ባነጋገረበት ወቅት ነው የአበበ ቢቂላ ስታዲየም ምርጫቸው አድርገዋል።
ከአምስት ዓመት በኋላ ከስደት የሚመለሰው የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን የአፍሪካ ዋንጫ የማጣሪያ ጨዋታውን ድሬዳዋ ላይም ያደርጋል።
ወርልድ ስፖርት (ጋዜጠኛ ጥሩነህ ካሳ)
#ethiopia #getutemesgen #getunews #worldsport #cafethiopianstadium
#ethiopia | ሁለት የኢትዮጵያ ስታዲዬሞች ኢንተርናሽናል ጨዋታ እንዲያስተናግዱ የካፍን ይሁንታ አገኙ
የአፍሪካን እግር ኳስ በበላይነት የሚያስተዳድረው ካፍ ለአዲሱ የውድድርዓመት ኢንተርናሽናል ጨዋታዎችን እንዲያስተናግዱ ይሁንታ የፈቀደላቸውን ሃገራት ይፋ አድርጓል።
ኢትዬጵያም በሚያስገርም ሁኔታ ሁለት ስታዲዬሞች ኢንተርናሽናል ጨዋታ ኢንዲያስተናግዱ ፍቃድ አግኝተዋል ተብሏል።
ካፍ ይፋ ባደረገው መረጃ መሰረት የድሬዳዋ እና የአበበ ቢቂላስታዲየም ኢንተርናሽናል ጨዋታ እንዲያስተናገዱ መፈቀዱ ይነገራል።
ይህ ደግሞ ለክለቦቻችንና ለብሄራዊ ቡድኑ መልካም አጋጣሚ የሚፈጥር ከመሆኑ ባሻገር ከስደት የሚታደግ ይሆናል።
በሚቀጥለው ወር መጨረሻ ኢንተርናሽናል ጨዋታ የሚጠብቃቸው ሲዳማ ቡና እና ወልዋሎ ጨዋታቸውን በአበበ ቢቂላ ስታዲየም ለማድረግ መወሰናቸው ታውቋል።
እግር ኳስ ፌዴሬሽኑ ሁለቱን ክለቦች ጠርቶ ባነጋገረበት ወቅት ነው የአበበ ቢቂላ ስታዲየም ምርጫቸው አድርገዋል።
ከአምስት ዓመት በኋላ ከስደት የሚመለሰው የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን የአፍሪካ ዋንጫ የማጣሪያ ጨዋታውን ድሬዳዋ ላይም ያደርጋል።
ወርልድ ስፖርት (ጋዜጠኛ ጥሩነህ ካሳ)
#ethiopia #getutemesgen #getunews #worldsport #cafethiopianstadium
1 month ago
ሲዳማ ቡና የኢትዮጵያ የፕሪሚየር ሊግ ዋንጫን አነሳ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 28፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ሲዳማ ቡና የ2018 ዓ.ም የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዋንጫን በዛሬው ዕለት ተረክቧል።
ሲዳማ ቡና ከኢትዮ ኤሌክትሪክ ባደረጉት ጨዋታ በዛሬው ዕለት ፍጻሜውን ያገኘው የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ በሲዳማ ቡና ሻምፒዮንነት ተጠናቅቋል።
በፕሪሚየር ሊግ ተሳትፎ ታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ ሻምፒዮን መሆኑን በ36ኛው ሳምንት ላይ ያረጋገጠው ሲዳማ ቡና፤ ዛሬ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በደጋፊዎቹ ፊት ዋንጫውን ከፍ አድርጓል።
የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ዲኤታ አቶ መኪዩ ሙሐመድ እና የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ኢሳያስ ጂራን ጨምሮ ከፍተኛ የመንግስት እና የተለያዩ ተቋማት ኃላፊዎች በሥነ ሥርዓቱ ላይ ተገኝተዋል።
በሊጉ የመጨረሻ ሳምንት እና የመጨረሻ ጨዋታ መርሐ ግብር ኢትዮ ኤሌክትሪክ የሊጉ ሻምፒዮን ሲዳማ ቡናን 1 ለ 0 አሸንፏል።
ምድረ ገነት ሽረ፣ ድሬዳዋ ከተማ፣ መቐለ 70 እንደርታ እና አርባ ምንጭ ከተማ ወደ ከፍተኛ ሊጉ የወረዱ ቡድኖች መሆናቸው ይታወቃል፡፡
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 28፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ሲዳማ ቡና የ2018 ዓ.ም የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዋንጫን በዛሬው ዕለት ተረክቧል።
ሲዳማ ቡና ከኢትዮ ኤሌክትሪክ ባደረጉት ጨዋታ በዛሬው ዕለት ፍጻሜውን ያገኘው የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ በሲዳማ ቡና ሻምፒዮንነት ተጠናቅቋል።
በፕሪሚየር ሊግ ተሳትፎ ታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ ሻምፒዮን መሆኑን በ36ኛው ሳምንት ላይ ያረጋገጠው ሲዳማ ቡና፤ ዛሬ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በደጋፊዎቹ ፊት ዋንጫውን ከፍ አድርጓል።
የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ዲኤታ አቶ መኪዩ ሙሐመድ እና የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ኢሳያስ ጂራን ጨምሮ ከፍተኛ የመንግስት እና የተለያዩ ተቋማት ኃላፊዎች በሥነ ሥርዓቱ ላይ ተገኝተዋል።
በሊጉ የመጨረሻ ሳምንት እና የመጨረሻ ጨዋታ መርሐ ግብር ኢትዮ ኤሌክትሪክ የሊጉ ሻምፒዮን ሲዳማ ቡናን 1 ለ 0 አሸንፏል።
ምድረ ገነት ሽረ፣ ድሬዳዋ ከተማ፣ መቐለ 70 እንደርታ እና አርባ ምንጭ ከተማ ወደ ከፍተኛ ሊጉ የወረዱ ቡድኖች መሆናቸው ይታወቃል፡፡
1 month ago
ከ170 በላይ ለጎርፍ አደጋ ተጋላጭ የሆኑ ሰዎች እንዲነሱ መደረጉ ተገለፀ
በድሬዳዋ በክረምት ወቅት በተለያየ ጊዜ ጎርፍ እንደሚከሰት የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር መንገዶች ባለስልጣን አስታውቋል።
የባለስልጣኑ ስራ አስኪያጅ አቶ ቴዎድሮስ ፍቅሬ እንደገለፁት ይህ ሁኔታ ዳግም አደጋ እንዳያስከትል ስድስት ቦታዎችን ቀድሞ በመለየት የተለያዩ ስራዎች መሰራታቸውን ተናግረዋል።
የችግሩን አሳሳቢነት በመረዳት በበጋ ወቅት ጀምሮ ለጎርፍ አደጋ ተጋላጭ ናቸው ተብለው የተለዩ ከ 170 በላይ ሰዎች ለጊዜያዊነት ወደ ሌላ ቦታ እንዲሰፍሩ መደረጉን ገልፀዋል።
ጎርፍ የሚበዛባቸው አካባቢዎች አስቀድሞ እርከን እየተሰራላቸው እንደሆነና በከተማዋ ከጥገና ባለፈ ማህበረሰቡ በቂ የሆነ ግንዛቤ እንዲያገኝ እየተደረገ መሆኑንም አስረድተዋል።
ከዚህ በፊት በከተማዋ የጎርፍ አደጋ ሲከሰት ብዙ ንብረትን ጨምሮ በሰዎች ላይ ከፍተኛ የሆነ ጉዳት እንደሚያስከትል የገለፁት አቶ ቴዎድሮስ፣ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ይህ ችግር እየተቀረፈ መምጣቱን ገልጸዋል።
አሐዱ_
በድሬዳዋ በክረምት ወቅት በተለያየ ጊዜ ጎርፍ እንደሚከሰት የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር መንገዶች ባለስልጣን አስታውቋል።
የባለስልጣኑ ስራ አስኪያጅ አቶ ቴዎድሮስ ፍቅሬ እንደገለፁት ይህ ሁኔታ ዳግም አደጋ እንዳያስከትል ስድስት ቦታዎችን ቀድሞ በመለየት የተለያዩ ስራዎች መሰራታቸውን ተናግረዋል።
የችግሩን አሳሳቢነት በመረዳት በበጋ ወቅት ጀምሮ ለጎርፍ አደጋ ተጋላጭ ናቸው ተብለው የተለዩ ከ 170 በላይ ሰዎች ለጊዜያዊነት ወደ ሌላ ቦታ እንዲሰፍሩ መደረጉን ገልፀዋል።
ጎርፍ የሚበዛባቸው አካባቢዎች አስቀድሞ እርከን እየተሰራላቸው እንደሆነና በከተማዋ ከጥገና ባለፈ ማህበረሰቡ በቂ የሆነ ግንዛቤ እንዲያገኝ እየተደረገ መሆኑንም አስረድተዋል።
ከዚህ በፊት በከተማዋ የጎርፍ አደጋ ሲከሰት ብዙ ንብረትን ጨምሮ በሰዎች ላይ ከፍተኛ የሆነ ጉዳት እንደሚያስከትል የገለፁት አቶ ቴዎድሮስ፣ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ይህ ችግር እየተቀረፈ መምጣቱን ገልጸዋል።
አሐዱ_
Sponsored by
Surafel
1 month ago
ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ተምሳሌት የሚሆን የብልጽግና ጉዞ ጀምራለች - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር)
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 27፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት ለመላው አፍሪካ ትልቅ ምሳሌ የሚሆን የብልጽግና ጉዞ ጀምራለች አሉ።
በገበታ ለትውልድ መርሐ ግብር የተገነባው የአርባምንጭ ኮንፈረንስ ሪዞርት በዛሬው ዕለት ተመርቆ በይፋ ሥራ ጀምሯል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዚሁ ወቅት ባስተላለፉት መልዕክት፥ በሐምሌና በነሐሴ ወራት የሚከሰተውን የክረምት ቁር ለመሸሽ ምቹ የሆነችው አርባምንጭ ጎብኝዎችን በሁለት እጆቿ ተቀብላ ለማስተናገድ ዝግጁ ሆናለች ብለዋል።
ከተማዋ በሪዞርቶቿና በተፈጥሮ ውበቶቿ ብቻ ሳይሆን በባህላዊ ምግቦቿ እንግዶችን ለመቀበል መዘጋጀቷን ተናግረዋል።
ሰዎች ወደ ከተማዋ የሚመጡት ለመዝናናት ብቻ እንዳልሆነ ገልጸው ፥ በዚሁ አጋጣሚ እኛ ተጨማሪ የሀብት ልማት እንዲፈጠር ማድረግ ይገባናል ነው ያሉት።
በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ሀገራቸው እያስመዘገበችው ያለውን አህጉራዊ አርአያነት ተመልክተው ወደ ሀገራቸው ተመልሰው ለመኖር ማሰብ የሚጀምሩበት ጊዜ ሩቅ አይደለም ብለዋል፡፡
የኢትዮጵያን ብልጽግና እውን ማድረግ ከእያንዳንዱ ዜጋ የሚጠበቅ ታሪካዊ ተግባር እንደሆነም አጽንኦት ሰጥተዋል፡፡
ኢትዮጵያ ወደ ፊት እንዳትራመድና ወደ ኋላ እንድትጎተት የሚፈልጉ የውስጥና የውጭ ኃይሎች የሚፈጥሯቸው ፈተናዎችና ችግሮች ቢኖሩም፤ ልማት፣ ሰላምና ብልጽግናን ስለምናስብ እያሸነፍን ጉዟችን እንቀጥላለን ሲሉ አስገንዝበዋል፡፡
ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት በ10 ነጥብ 2 በመቶ በሆነ ከፍተኛ ፍጥነት በማደግ ላይ የምትገኝ ብቸኛ ሀገር መሆኗን ገልጸው፥ ይህ ስኬት ለመላው ሕዝብ ኩራት በመሆኑ እንኳን ደስ አላችሁ ብለዋል።
ኢትዮጵያ ልጆቿን የምትሰበስብ፣ የአንድነትና የሰላም ምሳሌ ሆና እንደምትቀጥል ጠቅላይ ሚኒስትሩ አረጋግጠዋል።
ይህ የአህጉሪቱ ምሳሌ የሆነው ዕድገት በተግባር የሚታይባቸውን እንደ አርባምንጭ፣ ጅማ፣ ሶዶ፣ ሀዋሳ፣ ነቀምቴ፣ ባሕርዳር፣ ድሬዳዋና ጅግጅጋ ያሉ በርካታ ከተሞች በምስክርነት ጠቅሰዋል።
በሶስና አለማየሁ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 27፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት ለመላው አፍሪካ ትልቅ ምሳሌ የሚሆን የብልጽግና ጉዞ ጀምራለች አሉ።
በገበታ ለትውልድ መርሐ ግብር የተገነባው የአርባምንጭ ኮንፈረንስ ሪዞርት በዛሬው ዕለት ተመርቆ በይፋ ሥራ ጀምሯል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዚሁ ወቅት ባስተላለፉት መልዕክት፥ በሐምሌና በነሐሴ ወራት የሚከሰተውን የክረምት ቁር ለመሸሽ ምቹ የሆነችው አርባምንጭ ጎብኝዎችን በሁለት እጆቿ ተቀብላ ለማስተናገድ ዝግጁ ሆናለች ብለዋል።
ከተማዋ በሪዞርቶቿና በተፈጥሮ ውበቶቿ ብቻ ሳይሆን በባህላዊ ምግቦቿ እንግዶችን ለመቀበል መዘጋጀቷን ተናግረዋል።
ሰዎች ወደ ከተማዋ የሚመጡት ለመዝናናት ብቻ እንዳልሆነ ገልጸው ፥ በዚሁ አጋጣሚ እኛ ተጨማሪ የሀብት ልማት እንዲፈጠር ማድረግ ይገባናል ነው ያሉት።
በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ሀገራቸው እያስመዘገበችው ያለውን አህጉራዊ አርአያነት ተመልክተው ወደ ሀገራቸው ተመልሰው ለመኖር ማሰብ የሚጀምሩበት ጊዜ ሩቅ አይደለም ብለዋል፡፡
የኢትዮጵያን ብልጽግና እውን ማድረግ ከእያንዳንዱ ዜጋ የሚጠበቅ ታሪካዊ ተግባር እንደሆነም አጽንኦት ሰጥተዋል፡፡
ኢትዮጵያ ወደ ፊት እንዳትራመድና ወደ ኋላ እንድትጎተት የሚፈልጉ የውስጥና የውጭ ኃይሎች የሚፈጥሯቸው ፈተናዎችና ችግሮች ቢኖሩም፤ ልማት፣ ሰላምና ብልጽግናን ስለምናስብ እያሸነፍን ጉዟችን እንቀጥላለን ሲሉ አስገንዝበዋል፡፡
ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት በ10 ነጥብ 2 በመቶ በሆነ ከፍተኛ ፍጥነት በማደግ ላይ የምትገኝ ብቸኛ ሀገር መሆኗን ገልጸው፥ ይህ ስኬት ለመላው ሕዝብ ኩራት በመሆኑ እንኳን ደስ አላችሁ ብለዋል።
ኢትዮጵያ ልጆቿን የምትሰበስብ፣ የአንድነትና የሰላም ምሳሌ ሆና እንደምትቀጥል ጠቅላይ ሚኒስትሩ አረጋግጠዋል።
ይህ የአህጉሪቱ ምሳሌ የሆነው ዕድገት በተግባር የሚታይባቸውን እንደ አርባምንጭ፣ ጅማ፣ ሶዶ፣ ሀዋሳ፣ ነቀምቴ፣ ባሕርዳር፣ ድሬዳዋና ጅግጅጋ ያሉ በርካታ ከተሞች በምስክርነት ጠቅሰዋል።
በሶስና አለማየሁ
1 month ago
በድሬዳዋ ሐብታቸውን ለመውረስ አባቱን የገደለው ግለሰብ በሞት ፍርድ ተፈረደበት
👉ተባባሪው ደግሞ በ20 ዓመት ፅኑ እስራት ተቀጣ።
ሚያዝያ 23 ቀን 2016 ዓ.ም እኩለ ሌሊት ላይ አንደኛ ተከሳሽ ቤካ ኑረዲን ከአዲስ አበባ በምስጢር መጥቶ ከጓደኛው ሊበን ወንደሰን ጋር በመሆን አባቱን ማሪያም ኮንዶሚኒየም አካባቢ በጭካኔ ገድሏል።
ወንጀለኞቹ ድርጊቱን ፈጽመው ወደ አዲስ አበባ በግል መኪና ቢሰወሩም፣ የድሬዳዋ ፖሊስ ባደረገው ረቂቅ ክትትል በአጭር ጊዜ ውስጥ በቁጥጥር ስር ውለዋል።
የፌዴራል ፍትህ ሚኒስቴር አቃቤ ህግ ያቀረበውን ጠንካራ የሰውና የሰነድ ማስረጃ የመረመረው የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ድሬዳዋ ምድብ 4ኛ ወንጀል ችሎት፣ ሰኔ 25 ቀን 2018 ዓ.ም ውሳኔውን አስተላልፏል።
በዚህም መሰረት በዋና ወንጀለኛው ቤካ ላይ የሞት ፍርድ፣ በተባባሪው ሊበን ላይ ደግሞ የ20 ዓመት ፅኑ እስራት ተፈርዶባቸዋል።
Seledadotio
Seledadotio
👉ተባባሪው ደግሞ በ20 ዓመት ፅኑ እስራት ተቀጣ።
ሚያዝያ 23 ቀን 2016 ዓ.ም እኩለ ሌሊት ላይ አንደኛ ተከሳሽ ቤካ ኑረዲን ከአዲስ አበባ በምስጢር መጥቶ ከጓደኛው ሊበን ወንደሰን ጋር በመሆን አባቱን ማሪያም ኮንዶሚኒየም አካባቢ በጭካኔ ገድሏል።
ወንጀለኞቹ ድርጊቱን ፈጽመው ወደ አዲስ አበባ በግል መኪና ቢሰወሩም፣ የድሬዳዋ ፖሊስ ባደረገው ረቂቅ ክትትል በአጭር ጊዜ ውስጥ በቁጥጥር ስር ውለዋል።
የፌዴራል ፍትህ ሚኒስቴር አቃቤ ህግ ያቀረበውን ጠንካራ የሰውና የሰነድ ማስረጃ የመረመረው የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ድሬዳዋ ምድብ 4ኛ ወንጀል ችሎት፣ ሰኔ 25 ቀን 2018 ዓ.ም ውሳኔውን አስተላልፏል።
በዚህም መሰረት በዋና ወንጀለኛው ቤካ ላይ የሞት ፍርድ፣ በተባባሪው ሊበን ላይ ደግሞ የ20 ዓመት ፅኑ እስራት ተፈርዶባቸዋል።
Seledadotio
Seledadotio
1 month ago
አዲስ አበባ ክልል ልትሆን? ሕገ መንግስቱም ሊቀየር ነው?
ገዢው ብልጽግና ፓርቲ ከሰሞኑ በአዳማ ከተማ የማዕከላዊ ኮሚቴ ስብሰባውን ማድረጉ እየተሰማ ነው፡፡
ፓርቲው በይፋዊ ገጹ ላይ ባያረጋግጠው ስብሰባ መቀመጡን የሚገልጹ መረጃዎች እየወጡ ነው፡፡
አንዳንድ ያልተረጋገጡ መረጃዎች እንዳመላከቱት ብልጽግና በዚህ ስብሰባው ሕገ መንግስቱን ለመቀየር፣ አዲስአበባ እና ድሬዳዋ ከተማ አስተዳደርን ክልል ለማድረግ፣ የመሬት ፖሊሲን ለመቀየር፣ ስርአቱ ከፓርላሜንታዊ ወደ ፕሬዝዳንታዊ እንዲሆን መወሰኑ እየተሰማ ነው፡፡
እነዚህን መረጃዎችን በተመለከተ በይፋ የተረጋገጠ መረሃ ማግኘት ባይቻልም፤ እነዚህ ውሳኔዎች እውነተኛ ከሆኑ ግን ማርሽ ቀያሪ ውሳኔዎች እንደሚሆኑ ይጠበቃል።
Seledadotio
Seledadotio
ገዢው ብልጽግና ፓርቲ ከሰሞኑ በአዳማ ከተማ የማዕከላዊ ኮሚቴ ስብሰባውን ማድረጉ እየተሰማ ነው፡፡
ፓርቲው በይፋዊ ገጹ ላይ ባያረጋግጠው ስብሰባ መቀመጡን የሚገልጹ መረጃዎች እየወጡ ነው፡፡
አንዳንድ ያልተረጋገጡ መረጃዎች እንዳመላከቱት ብልጽግና በዚህ ስብሰባው ሕገ መንግስቱን ለመቀየር፣ አዲስአበባ እና ድሬዳዋ ከተማ አስተዳደርን ክልል ለማድረግ፣ የመሬት ፖሊሲን ለመቀየር፣ ስርአቱ ከፓርላሜንታዊ ወደ ፕሬዝዳንታዊ እንዲሆን መወሰኑ እየተሰማ ነው፡፡
እነዚህን መረጃዎችን በተመለከተ በይፋ የተረጋገጠ መረሃ ማግኘት ባይቻልም፤ እነዚህ ውሳኔዎች እውነተኛ ከሆኑ ግን ማርሽ ቀያሪ ውሳኔዎች እንደሚሆኑ ይጠበቃል።
Seledadotio
Seledadotio
1 month ago
ማስታወቂያ
👌 ለየትኛውም አይነት ሜዳ አስተማማኝ ማሊያ! 👌
👇👇 የት አገኛለው ካሉ 👇👇
አድራሻ (አዲስ አበባ) :- 🏬 አዲስ አበባ ከትንሿ ስታዲየም አጠገብ አን ቢዝነስ ሴንተር 3ኛ ፎቅ
አድራሻ (ድሬዳዋ) :- 🏬 ድሬዳዋ ስታዲየም የመሸጫ ስፍራ ምድር ቤት
አድራሻ (አዳማ) :- 🏬 የአዳማ ከተማ አስተዳደር ፊት ለፊት የሚገኘው ካናብ ሞል 1ኛ ፎቅ
አድራሻ (ባህር ዳር ) :- 🏬 ቀበሌ 4 ጊዮርጊስ ህንፃ ፊት ለፊት ወደብ ህንፃ 1ኛ ፎቅ
አድራሻ (ሆሳዕና) :- 🏬 ሀዲያ ዞን ፋይናንስ ጵ/ቤት ፊት ለፊት ሴች ዱና ሞል
ለመረጃና ለትዕዛዝ (አዲስ አበባ) :-📱0900006363
ለመረጃና ለትዕዛዝ (ድሬዳዋ) :-📱0955495959
ለመረጃና ለትዕዛዝ (አዳማ) :-📱0951008686
ለመረጃና ለትዕዛዝ (ባህርዳር) :-📱0918004342
ለመረጃና ለትዕዛዝ (ሆሳዕና) :-📱0946555577
goferesportswear
👌 ለየትኛውም አይነት ሜዳ አስተማማኝ ማሊያ! 👌
👇👇 የት አገኛለው ካሉ 👇👇
አድራሻ (አዲስ አበባ) :- 🏬 አዲስ አበባ ከትንሿ ስታዲየም አጠገብ አን ቢዝነስ ሴንተር 3ኛ ፎቅ
አድራሻ (ድሬዳዋ) :- 🏬 ድሬዳዋ ስታዲየም የመሸጫ ስፍራ ምድር ቤት
አድራሻ (አዳማ) :- 🏬 የአዳማ ከተማ አስተዳደር ፊት ለፊት የሚገኘው ካናብ ሞል 1ኛ ፎቅ
አድራሻ (ባህር ዳር ) :- 🏬 ቀበሌ 4 ጊዮርጊስ ህንፃ ፊት ለፊት ወደብ ህንፃ 1ኛ ፎቅ
አድራሻ (ሆሳዕና) :- 🏬 ሀዲያ ዞን ፋይናንስ ጵ/ቤት ፊት ለፊት ሴች ዱና ሞል
ለመረጃና ለትዕዛዝ (አዲስ አበባ) :-📱0900006363
ለመረጃና ለትዕዛዝ (ድሬዳዋ) :-📱0955495959
ለመረጃና ለትዕዛዝ (አዳማ) :-📱0951008686
ለመረጃና ለትዕዛዝ (ባህርዳር) :-📱0918004342
ለመረጃና ለትዕዛዝ (ሆሳዕና) :-📱0946555577
goferesportswear
1 month ago
የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ሐምሌ 8/2018 ዓ/ም ለሚጀመረው ሀገራዊ ጉባዔ ለምክክር የቀረጻቸውን 8 አጀንዳዎች ይፋ አድርጓል።
ምክክር የሚደረግባቸው 8 የተመረጡ አጀንዳዎች የትኞቹ ናቸው ?
1) አጀንዳ ቁጥር 1 የሀገር ግንባታ ጉዳይ፣
2) አጀንዳ ቁጥር 2 የፖለቲካ ስርዓት፣ የመንግስት አደረጃጀትና ቅርጽ፣
3) አጀንዳ ቁጥር 3 የፌዴራል ከተሞች፥ አዲስ አበባና ድሬዳዋ
4) አጀንዳ ቁጥር 4 የሃይማኖት ጉዳዮች፣
5) አጀንዳ ቁጥር 5 የተቋማት ግንባታ የሕግ የበላይነትና ሰብዓዊ መብቶች፣
6) አጀንዳ ቁጥር 6 ማህበራዊ ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች፣ የአርሶ አደሮች እና የአርብቶ አደሮች ጉዳይ፣
7) አጀንዳ ቁጥር 7 ሙስና እና መልካም አስተዳደር
8) አጀንዳ ቁጥር 8 ሰላም ግንባታ
አጀንዳዎቹ በተለያዩ ክልሎች ከ200 ሺሕ በላይ ሰዎችን በማመካከር የተገኙ መሆናቸውን የኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር መስፍን ዓርዓያ ተናግረዋል።tikvah
Seledadotio
Seledadotio
ምክክር የሚደረግባቸው 8 የተመረጡ አጀንዳዎች የትኞቹ ናቸው ?
1) አጀንዳ ቁጥር 1 የሀገር ግንባታ ጉዳይ፣
2) አጀንዳ ቁጥር 2 የፖለቲካ ስርዓት፣ የመንግስት አደረጃጀትና ቅርጽ፣
3) አጀንዳ ቁጥር 3 የፌዴራል ከተሞች፥ አዲስ አበባና ድሬዳዋ
4) አጀንዳ ቁጥር 4 የሃይማኖት ጉዳዮች፣
5) አጀንዳ ቁጥር 5 የተቋማት ግንባታ የሕግ የበላይነትና ሰብዓዊ መብቶች፣
6) አጀንዳ ቁጥር 6 ማህበራዊ ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች፣ የአርሶ አደሮች እና የአርብቶ አደሮች ጉዳይ፣
7) አጀንዳ ቁጥር 7 ሙስና እና መልካም አስተዳደር
8) አጀንዳ ቁጥር 8 ሰላም ግንባታ
አጀንዳዎቹ በተለያዩ ክልሎች ከ200 ሺሕ በላይ ሰዎችን በማመካከር የተገኙ መሆናቸውን የኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር መስፍን ዓርዓያ ተናግረዋል።tikvah
Seledadotio
Seledadotio
1 month ago
ለከባድና ቀላል ጭነት መኪና ባለቤቶች: የጂፒኤስ መከታተያ ሥርዓት ቁልፍ ጥቅሞች 🚚📍
የጭነት መኪና ባለቤትነት፣ የከባድም ሆነ የቀላል ጭነት፣ ትልቅ ኢንቨስትመንት ነው። እነዚህ ተሽከርካሪዎች የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ የጀርባ አጥንት ሲሆኑ፣ የእነሱን እንቅስቃሴ በአግባቡ መቆጣጠር ለሥራው ስኬት ወሳኝ ነው።
በኢትዮጵያ በተለይ የነዳጅ ወጪ መናር፣ የመንገድ ሁኔታዎች እና የሎጂስቲክስ አስተዳደር የራሳቸው የሆኑ ፈተናዎች ሲሆኑ፣ የተሽከርካሪ ጂፒኤስ መከታተያ ሥርዓት ለእነዚህ ችግሮች ውጤታማ መፍትሄዎችን ይሰጣል።
ታዲያ የጂፒኤስ መከታተያ ሥርዓት ለከባድና ቀላል ጭነት መኪና ባለቤቶች የሚሰጣቸው ዋና ዋና ጥቅሞች ምንድን ናቸው? በአጭሩ እነሆ፦
የጭነት መኪናዎ ደህንነት እና ቅልጥፍና ያሳስብዎታል? ጂፒኤስ መከታተያ ዘመናዊ መፍትሄ ነው!
• ተሽከርካሪ ደህንነት 🔒: መኪናዎ የት እንዳለ በቅጽበት ይወቁ! ስርቆትን ለመከላከል እና ከተሰረቀ በፍጥነት ለማግኘት ይረዳል።
• ወጪ ቅነሳ 💰: የነዳጅ ፍጆታን ይቆጣጠሩ፣ አላስፈላጊ ወጪን ይቀንሱ። ትክክለኛውን መንገድ በመምረጥ ነዳጅ ይቆጥባሉ! ⛽
• የሥራ ቅልጥፍና 🚀: እያንዳንዱ መኪና የት እንዳለ በማወቅ ሥራዎችን በቀላሉ ያቀናብሩ። ለደንበኞችም ትክክለኛ መረጃ ይስጡ።
• አሽከርካሪ አስተዳደር 👨✈️: የአሽከርካሪዎችን የአነዳድ ዘይቤ እና የሥራ ሰዓት ይቆጣጠሩ። ደህንነትን ይጨምራል፣ ጉዳትን ይቀንሳል።
• የጥገና አስተዳደር 🛠️: የጥገና ጊዜን በማቀድ ድንገተኛ ብልሽቶችን ይቀንሱ።
በአጭሩ፣ ጂፒኤስ መከታተያ የንብረትዎን ደህንነት ለማረጋገጥ፣ ወጪ ለመቆጠብ፣ ቅልጥፍናን ለማሳደግ እና የአሽከርካሪዎችን ደህንነት ለመከታተል ወሳኝ ኢንቨስትመንት ነው! 💪
ሳሚ አውቶሞቲቭ - አስተማማኝ የመኪና ደህንነትዎ! 🛡️
🛠️ ይህን ዘመናዊ ቴክኖሎጂ ለማስገጠም እና ለበለጠ መረጃ አሁኑኑ ይደውሉልን! 📞
📲 ስልክ ቁጥሮች:
• 0912072874
• 0947329334
• 0913917373
• 0906015555
• 0906065151 (አዳማ)
• 0948110505 (ድሬዳዋ ቢሮ)
• +25111470 5763 (የደንበኞች አገልግሎት)
1 month ago
የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ሐምሌ 8/2018 ዓ/ም ለሚጀመረው ሀገራዊ ጉባዔ ለምክክር የቀረጻቸውን 8 አጀንዳዎች ይፋ አድርጓል።
ምክክር የሚደረግባቸው 8 የተመረጡ አጀንዳዎች የትኞቹ ናቸው ?
1) አጀንዳ ቁጥር 1 የሀገር ግንባታ ጉዳይ፣
2) አጀንዳ ቁጥር 2 የፖለቲካ ስርዓት፣ የመንግስት አደረጃጀትና ቅርጽ፣
3) አጀንዳ ቁጥር 3 የፌዴራል ከተሞች፥ አዲስ አበባና ድሬዳዋ
4) አጀንዳ ቁጥር 5 የሃይማኖት ጉዳዮች፣
5) አጀንዳ ቁጥር 6 የተቋማት ግንባታ የሕግ የበላይነትና ሰብዓዊ መብቶች፣
6) ማህበራዊ ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች፣ የአርሶ አደሮች እና የአርብቶ አደሮች ጉዳይ፣
7) ሙስና እና መልካም አስተዳደር
8) አጀንዳ ቁጥር 8 ሰላም ግንባታ
አጀንዳዎቹ በተለያዩ ክልሎች ከ200 ሺሕ በላይ ሰዎችን በማመካከር የተገኙ መሆናቸውን የኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር መስፍን ዓርዓያ ተናግረዋል።
ምክክር የሚደረግባቸው 8 የተመረጡ አጀንዳዎች የትኞቹ ናቸው ?
1) አጀንዳ ቁጥር 1 የሀገር ግንባታ ጉዳይ፣
2) አጀንዳ ቁጥር 2 የፖለቲካ ስርዓት፣ የመንግስት አደረጃጀትና ቅርጽ፣
3) አጀንዳ ቁጥር 3 የፌዴራል ከተሞች፥ አዲስ አበባና ድሬዳዋ
4) አጀንዳ ቁጥር 5 የሃይማኖት ጉዳዮች፣
5) አጀንዳ ቁጥር 6 የተቋማት ግንባታ የሕግ የበላይነትና ሰብዓዊ መብቶች፣
6) ማህበራዊ ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች፣ የአርሶ አደሮች እና የአርብቶ አደሮች ጉዳይ፣
7) ሙስና እና መልካም አስተዳደር
8) አጀንዳ ቁጥር 8 ሰላም ግንባታ
አጀንዳዎቹ በተለያዩ ክልሎች ከ200 ሺሕ በላይ ሰዎችን በማመካከር የተገኙ መሆናቸውን የኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር መስፍን ዓርዓያ ተናግረዋል።
1 month ago
ግልግል!
ግብር በቴሌብር!
ሰነድ ማዘጋጀትና ሰልፍ መሰለፍ ቀረ፤ የዓመቱን ግብር በቴሌብር አሁኑኑ እንክፈል!
የገቢዎች ሚኒስቴርን፣ የአዲስ አበባ (ከፍተኛ፣ መካከለኛና አነስተኛ)፣ የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደርን እንዲሁም የኦሮሚያ፣ የአማራ፣ የሲዳማ፣ የደቡብ ኢትዮጵያ፣ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ፣ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦችን፣ የሱማሌ፣ የሐረሪ፣ የአፋር እና የቤንሻንጉል ጉሙዝ ገቢዎች የግብር ክፍያ በአስተማማኝ ሁኔታ አሁኑኑ በቴሌብር ይክፈሉ!
ቴሌብር ሱፐርአፕን https://bit.ly/telebirr_Su... ጭነን ስንከፍል እንዲህ ነን!
#ደንበኛ_ስንሆን_እንዲህ_ነን #ስንመዘገብ_እንዲህ_ነን #ስንጭን_እንዲህ_ነን #ስናስጀምር_እንዲህ_ነን
ግብር በቴሌብር!
ሰነድ ማዘጋጀትና ሰልፍ መሰለፍ ቀረ፤ የዓመቱን ግብር በቴሌብር አሁኑኑ እንክፈል!
የገቢዎች ሚኒስቴርን፣ የአዲስ አበባ (ከፍተኛ፣ መካከለኛና አነስተኛ)፣ የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደርን እንዲሁም የኦሮሚያ፣ የአማራ፣ የሲዳማ፣ የደቡብ ኢትዮጵያ፣ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ፣ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦችን፣ የሱማሌ፣ የሐረሪ፣ የአፋር እና የቤንሻንጉል ጉሙዝ ገቢዎች የግብር ክፍያ በአስተማማኝ ሁኔታ አሁኑኑ በቴሌብር ይክፈሉ!
ቴሌብር ሱፐርአፕን https://bit.ly/telebirr_Su... ጭነን ስንከፍል እንዲህ ነን!
#ደንበኛ_ስንሆን_እንዲህ_ነን #ስንመዘገብ_እንዲህ_ነን #ስንጭን_እንዲህ_ነን #ስናስጀምር_እንዲህ_ነን
2 months ago
ሲዳማ ቡና ሻምፒዮንነቱን ለማረጋገጥ…
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 13፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ36ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር በዛሬው ዕለት ሦስት ጨዋታዎች ይደረጋሉ።
በአዲስ አበባ ስታዲየም ቀን 10 ሰዓት ላይ የሳምንቱ ተጠባቂ ጨዋታ በሲዳማ ቡና እና በነገሌ አርሲ መካከል ይደረጋል።
የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና ከዛሬው ጨዋታ አንድ ነጥብ የሚያገኝ ወይም ድል የሚያደርግ ከሆነ ቀሪ ሁለት መርሐ ግብሮች እያሉት ሻምፒዮን መሆኑን ያረጋግጣል።
በዚህም በታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ የሊጉ ሻምፒዮን ይሆናል።
ተጋጣሚው ነገሌ አርሲ ጨዋታውን የሚያሸንፍ ከሆነ ደግሞ በዋንጫ ፉክክር ውስጥ የሚቆይ ይሆናል።
ሲዳማ ቡናም የሊጉ ሻምፒዮንነቱን ለማረጋገጥ ቀጣይ ጨዋታዎችን ለመጠበቅ ይገደዳል።
ሲዳማ ቡና ከዚህ ቀደም በ2002 እና በ2011 ዓ.ም የሊጉን ዋንጫ ለማንሳት ተቃርቦ ሳይሳካለት መቅረቱ ይታወሳል።
በተመሳሳይ ስታዲየም ቀን 7 ሰዓት ላይ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከኢትዮጵያ ቡና ጨዋታቸውን ያደርጋሉ።
በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ደግሞ ቀን 10 ሰዓት ላይ ድሬዳዋ ከተማ ከሸገር ከተማ ይገናኛሉ።
ሲዳማ ቡና ሊጉን በ64 ነጥብ ሲመራ ነገሌ አርሲ በ56 ነጥብ ይከተላል።
አቤል ያለው እና ናትናኤል ዳንኤል በተመሳሳይ 14 ግቦች የሊጉን ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነት ደረጃ እየመሩ ይገኛሉ።
ታምራት ኢያሱ በ12 እንዲሁም አዲስ ግደይ በ11 ግቦች ይከተላሉ።
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 13፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ36ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር በዛሬው ዕለት ሦስት ጨዋታዎች ይደረጋሉ።
በአዲስ አበባ ስታዲየም ቀን 10 ሰዓት ላይ የሳምንቱ ተጠባቂ ጨዋታ በሲዳማ ቡና እና በነገሌ አርሲ መካከል ይደረጋል።
የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና ከዛሬው ጨዋታ አንድ ነጥብ የሚያገኝ ወይም ድል የሚያደርግ ከሆነ ቀሪ ሁለት መርሐ ግብሮች እያሉት ሻምፒዮን መሆኑን ያረጋግጣል።
በዚህም በታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ የሊጉ ሻምፒዮን ይሆናል።
ተጋጣሚው ነገሌ አርሲ ጨዋታውን የሚያሸንፍ ከሆነ ደግሞ በዋንጫ ፉክክር ውስጥ የሚቆይ ይሆናል።
ሲዳማ ቡናም የሊጉ ሻምፒዮንነቱን ለማረጋገጥ ቀጣይ ጨዋታዎችን ለመጠበቅ ይገደዳል።
ሲዳማ ቡና ከዚህ ቀደም በ2002 እና በ2011 ዓ.ም የሊጉን ዋንጫ ለማንሳት ተቃርቦ ሳይሳካለት መቅረቱ ይታወሳል።
በተመሳሳይ ስታዲየም ቀን 7 ሰዓት ላይ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከኢትዮጵያ ቡና ጨዋታቸውን ያደርጋሉ።
በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ደግሞ ቀን 10 ሰዓት ላይ ድሬዳዋ ከተማ ከሸገር ከተማ ይገናኛሉ።
ሲዳማ ቡና ሊጉን በ64 ነጥብ ሲመራ ነገሌ አርሲ በ56 ነጥብ ይከተላል።
አቤል ያለው እና ናትናኤል ዳንኤል በተመሳሳይ 14 ግቦች የሊጉን ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነት ደረጃ እየመሩ ይገኛሉ።
ታምራት ኢያሱ በ12 እንዲሁም አዲስ ግደይ በ11 ግቦች ይከተላሉ።
Sponsored by
Surafel
2 months ago
ኢትዮጵያ መድን ድሬዳዋ ከተማን አሸነፈ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 7፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ35ኛ ሳምንት ሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ኢትዮጵያ መድን ድሬዳዋ ከተማን 1 ለ 0 አሸንፏል፡፡
ምሽት 12 ሰዓት ላይ በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ወገኔ ገዛኸኝ የኢትዮጵያ መድንን ብቸኛ የማሸነፊያ ግብ አስቆጥሯል፡፡
ቀደም ሲል በተደረጉ የሊጉ ጨዋታዎች ሲዳማ ቡና ኢትዮጵያ ቡናን 2 ለ 1 እንዲሁም ቅዱስ ጊዮርጊስ መቻልን 3 ለ 0 አሸንፈዋል።
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 7፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ35ኛ ሳምንት ሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ኢትዮጵያ መድን ድሬዳዋ ከተማን 1 ለ 0 አሸንፏል፡፡
ምሽት 12 ሰዓት ላይ በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ወገኔ ገዛኸኝ የኢትዮጵያ መድንን ብቸኛ የማሸነፊያ ግብ አስቆጥሯል፡፡
ቀደም ሲል በተደረጉ የሊጉ ጨዋታዎች ሲዳማ ቡና ኢትዮጵያ ቡናን 2 ለ 1 እንዲሁም ቅዱስ ጊዮርጊስ መቻልን 3 ለ 0 አሸንፈዋል።
2 months ago
በ25 ድምፅ ወደ ምክር ቤት፤ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ እጅግ ዝቅተኛ በሆነ የድምፅ ቁጥር የተመረጡ ተፎካካሪ ዕጩዎች መኖራቸው ታወቀ!
ምርጫ ቦርድ ባወጣቸው ተከታታይ መግለጫዎች ያጸደቃቸው ከፊል ውጤቶች፣ በርካታ ተፎካካሪ በሌለባቸው የምርጫ ክልሎች የሚወዳደሩ የተቃዋሚ ዕጩዎች እጅግ ዝቅተኛ በሆነ የመራጮች ድምፅ ወደ ምክር ቤቶች መግባታቸውን አሳይተዋል።
ከእነዚህ መካከል ለድሬዳዋ ከተማ ምክር ቤት በኩርቱ የምርጫ ክልል የተመረጡት የነፃነትና እኩልነት ፓርቲ ዕጩ አቶ ጀማል ኡመር ኢብራሂም፣ ከተመዘገቡት 2,204 መራጮች መካከል ያገኙት ድምፅ 25 ብቻ (1% ገደማ) እንደሆነ ተገልጿል።
በጀሎበጂና የምርጫ ክልልም የአዲስ ትውልድ ፓርቲ ተወካዩ አቶ ረመዳን መሐመድ ሰኢድ 200 ድምፅ (3%) ብቻ በማግኘት ወደ ምክር ቤት መግባት ችለዋል።ለዚህም ዋነኛው ምክንያት በእነዚህ የምርጫ ክልሎች ከወንበሮቹ ቁጥር እኩል ከሆኑት ዕጩዎች ውጪ ሌላ ተወዳዳሪ ፓርቲ ባለመኖሩ ነው።
እስካሁን ከተመረጡት 8 ተቃዋሚዎች መካከል እውነተኛ የአብላጫ ድምፅ (ከ50% በላይ) ያገኙት የኦብነግ ተወካይ አቶ መሀሙድ ሀሰን (73%) እና የአብን ዕጩ አቶ ጣሂር መሀመድ (59%) ብቻ ሲሆኑ፣ ቀሪዎቹ 6ቱ ዕጩዎች የኢዜማውን መሪ አቶ እዮብ መሳፍንትን (42%) ጨምሮ ከ50% በታች ድምፅ አግኝተዋል።ስምንቱም የተቃዋሚ ወኪሎች ያሸነፏቸው ወንበሮች ብልፅግና ፓርቲ ውክልናን ለማሳደግ በሚል ሆነ ብሎ ዕጩ ያላቀረበባቸው መሆኑ ታውቋል።
ኢትዮጵያ ኢንሳይደር
Seledadotio
Seledadotio
ምርጫ ቦርድ ባወጣቸው ተከታታይ መግለጫዎች ያጸደቃቸው ከፊል ውጤቶች፣ በርካታ ተፎካካሪ በሌለባቸው የምርጫ ክልሎች የሚወዳደሩ የተቃዋሚ ዕጩዎች እጅግ ዝቅተኛ በሆነ የመራጮች ድምፅ ወደ ምክር ቤቶች መግባታቸውን አሳይተዋል።
ከእነዚህ መካከል ለድሬዳዋ ከተማ ምክር ቤት በኩርቱ የምርጫ ክልል የተመረጡት የነፃነትና እኩልነት ፓርቲ ዕጩ አቶ ጀማል ኡመር ኢብራሂም፣ ከተመዘገቡት 2,204 መራጮች መካከል ያገኙት ድምፅ 25 ብቻ (1% ገደማ) እንደሆነ ተገልጿል።
በጀሎበጂና የምርጫ ክልልም የአዲስ ትውልድ ፓርቲ ተወካዩ አቶ ረመዳን መሐመድ ሰኢድ 200 ድምፅ (3%) ብቻ በማግኘት ወደ ምክር ቤት መግባት ችለዋል።ለዚህም ዋነኛው ምክንያት በእነዚህ የምርጫ ክልሎች ከወንበሮቹ ቁጥር እኩል ከሆኑት ዕጩዎች ውጪ ሌላ ተወዳዳሪ ፓርቲ ባለመኖሩ ነው።
እስካሁን ከተመረጡት 8 ተቃዋሚዎች መካከል እውነተኛ የአብላጫ ድምፅ (ከ50% በላይ) ያገኙት የኦብነግ ተወካይ አቶ መሀሙድ ሀሰን (73%) እና የአብን ዕጩ አቶ ጣሂር መሀመድ (59%) ብቻ ሲሆኑ፣ ቀሪዎቹ 6ቱ ዕጩዎች የኢዜማውን መሪ አቶ እዮብ መሳፍንትን (42%) ጨምሮ ከ50% በታች ድምፅ አግኝተዋል።ስምንቱም የተቃዋሚ ወኪሎች ያሸነፏቸው ወንበሮች ብልፅግና ፓርቲ ውክልናን ለማሳደግ በሚል ሆነ ብሎ ዕጩ ያላቀረበባቸው መሆኑ ታውቋል።
ኢትዮጵያ ኢንሳይደር
Seledadotio
Seledadotio
2 months ago
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽነር መስፍን አርዓያ (ፕ/ር) የኮሚሽኑ ሥራ የደረሰበትን ታሪካዊ ምዕራፍ አስመልክቶ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ያነሷቸው ነጥቦች፡-
👉 ኢትዮጵያ አሳታፊና አካታች ሀገራዊ ምክክር ሂደት ውስጥ ከገባች አራት ዓመታት ተቆጥረዋል
👉 በእነዚህ ዓመታት ውስጥ ወደ ምክክር ጉባኤ የሚያደርሱ መሰረታዊ ተግባራት ተከናውነዋል
👉 በመላው ሀገሪቱ 1ሺህ 234 ወረዳዎችን ማሳተፍ ተችሏል
👉 ይህም በሀገሪቱ ካሉ አካባቢዎች 93 በመቶውን የሚሸፍን ነው
👉 በ12 ክልሎች፣ በአዲስ አበባ እና ድሬዳዋ ከተማ አስተዳደሮች እንዲሁም ከፌደራል ባለድርሻ አካላት ስኬታማ የአጀንዳ ማሰባሰብ ተግባር ተከናውኗል
👉 በውጭ ሀገር የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን እንዲሳተፉ ተደርጓል
👉 አጀንዳ የተሰባሰበባቸው አካባቢዎች ለዋናው ጉባኤ የሚወክላቸውን መርጠዋል
👉 የምክር ሂደቱ ከጅምሩ አንስቶ ግልጽ፣ ገለልተኛና አሳታፊ በሆነ አሰራር እንዲመራ ተደርጓል
👉 የኢትዮጵያ ሕዝብ ለሂደቱ የሰጠው ትኩረትና ያሳየው የባለቤትነት መንፈስ እጅግ የሚያበረታታ ነው
👉 የኢትዮጵያ ሕዝብ በምክክር ሂደቱ ታሪክ የማይረሳው ሀገራዊ ኃላፊነት ተወጥቷል
👉 ሀገራዊ የምክክር ጉባኤው በመጪው ሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ይጀመራል
👉 ጉባኤው በአዲስ አበባ ከተማ ለሦስት ተከታታይ ሳምንታት ይካሄዳል
👉 ኢትዮጵያ አሳታፊና አካታች ሀገራዊ ምክክር ሂደት ውስጥ ከገባች አራት ዓመታት ተቆጥረዋል
👉 በእነዚህ ዓመታት ውስጥ ወደ ምክክር ጉባኤ የሚያደርሱ መሰረታዊ ተግባራት ተከናውነዋል
👉 በመላው ሀገሪቱ 1ሺህ 234 ወረዳዎችን ማሳተፍ ተችሏል
👉 ይህም በሀገሪቱ ካሉ አካባቢዎች 93 በመቶውን የሚሸፍን ነው
👉 በ12 ክልሎች፣ በአዲስ አበባ እና ድሬዳዋ ከተማ አስተዳደሮች እንዲሁም ከፌደራል ባለድርሻ አካላት ስኬታማ የአጀንዳ ማሰባሰብ ተግባር ተከናውኗል
👉 በውጭ ሀገር የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን እንዲሳተፉ ተደርጓል
👉 አጀንዳ የተሰባሰበባቸው አካባቢዎች ለዋናው ጉባኤ የሚወክላቸውን መርጠዋል
👉 የምክር ሂደቱ ከጅምሩ አንስቶ ግልጽ፣ ገለልተኛና አሳታፊ በሆነ አሰራር እንዲመራ ተደርጓል
👉 የኢትዮጵያ ሕዝብ ለሂደቱ የሰጠው ትኩረትና ያሳየው የባለቤትነት መንፈስ እጅግ የሚያበረታታ ነው
👉 የኢትዮጵያ ሕዝብ በምክክር ሂደቱ ታሪክ የማይረሳው ሀገራዊ ኃላፊነት ተወጥቷል
👉 ሀገራዊ የምክክር ጉባኤው በመጪው ሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ይጀመራል
👉 ጉባኤው በአዲስ አበባ ከተማ ለሦስት ተከታታይ ሳምንታት ይካሄዳል
2 months ago
የዓለም ዋንጫ : በኮካ ኮላ
#ethiopia | የዓለም ዋንጫ መክፈቻን አስመልክቶ የኮካ ኮላ ኩባንያ ያዘጋጀው ደማቅ የምሽት መርሃ ግብር በአዲስ አበባ ስካይላይት ሆቴል እየተካሄደ ነው
የኮካ ኮላ ኩባንያ ከፊፋ የዓለም ዋንጫ ጋር የዘለቀውን የግማሽ ክፍለ ዘመን ታሪካዊ አጋርነት ለመዘከርና የዘንድሮውን 23ኛውን ዓለም አቀፍ የእግር ኳስ ውድድር መጀመር ለማብሰር ያዘጋጀው ልዩ የክብር ምሽት በአዲስ አበባ ስካይላይት ሆቴል በመካሄድ ላይ ይገኛል።
ይህ ታላቅ መርሃ ግብር በዓለም ዙሪያ የሚገኙ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ የስፖርት አፍቃሪዎች የውድድሩን መክፈቻ ስነ ስርዓትና የመጀመሪያ ጨዋታ ለመታደም በአንድነት ከሚሰበሰቡበት ታሪካዊ ቅጽበት ጋር ተስማሚ በሆነ መልኩ እየተከናወነ ነው።
በዚህ ማራኪ ድባብ ባለው መድረክ ላይ በርካታ ታዋቂ ሰዎች፣ የኪነጥበብ ባለሙያዎች፣ የስፖርት ቤተሰቦችና ጋዜጠኞች ተገኝተው ምሽቱን በልዩ የሙዚቃ ዝግጅቶች፣ የፈጠራ ስራዎችና የተለያዩ መዝናኛዎች እያደመቁት ይገኛሉ።
በመርሐግብሩ ላይ ንግግር ያደረጉት የኮካ ኮላ ሲኒየር ማርኬቲንግ ማናጀር ሜሮን ብርሃኑ እግር ኳስ ከስፖርትነቱ ባለፈ ሰዎችን በጋራ ስሜትና ፍቅር የሚያስተሳስር ሁለንተናዊ ቋንቋ መሆኑን ገልጸዋል።
የ2026ቱ የፊፋ የዓለም ዋንጫ በታሪክ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ሀገራትና ጨዋታዎች የሚስተናገዱበት ግዙፍ ውድድር መሆኑን የጠቆሙት ማናጀሯ፣ ኮካ ኮላ ትርጉም ባላቸው አቀራረቦች የኢትዮጵያን እግር ኳስ አፍቃሪዎች ከውድድሩ ደስታ ጋር ይበልጥ ለማገናኘት ቁርጠኛ መሆኑን አብራርተዋል።
በሌላ በኩል የኮካ ኮላ ቢቨሬጅስ አፍሪካ ተወካይ በበኩላቸው ኩባንያው በኢትዮጵያ ስላለው ጠንካራ ተሳትፎና ምርት ስርጭት ማብራሪያ ሰጥተዋል።
በአሁኑ ወቅት በሀገሪቱ አምስት ፋብሪካዎች እንደሚንቀሳቀሱና ከእነዚህም ውስጥ በአዲስ አበባ፣ ሰበታ፣ ባሕር ዳር እንዲሁም በድሬዳዋ የሚገኙት አራቱ ፋብሪካዎች የኮካ ኮላ ምርቶችን በሙሉ አቅማቸው እያመረቱ ለገበያ እያቀረቡ እንደሚገኝ አስታውቀዋል።
ከማሸጊያ ጋር በተያያዘም ለተለያዩ የደንበኞች ፍላጎት ተስማሚ የሆኑ ከ300 ሚሊ ሊትር ተመላሽ የብርጭቆ ጠርሙስ ጀምሮ ለጉዞ የሚመቹ የ350 እና የ500 ሚሊ ሊትር እንዲሁም ለቤተሰብና ለስብሰባዎች የሚሆኑ የ1.5 ሊትር የፒኢቲ ማሸጊያዎችን እያቀረቡ መሆኑን አስረድተዋል።
የዓለም ዋንጫውን ታላቅ ስሜትና የኮካ ኮላን ደማቅ ድባብ በቀጥታ ወደ እናንተ ማድረሳችንን እንቀጥላለን።
ውጤት
60" ሜክሲኮ 1 - 0 ደቡብ አፍሪካ
#worldcup #cocacola #football #skylighthotel #fifaworldcup #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | የዓለም ዋንጫ መክፈቻን አስመልክቶ የኮካ ኮላ ኩባንያ ያዘጋጀው ደማቅ የምሽት መርሃ ግብር በአዲስ አበባ ስካይላይት ሆቴል እየተካሄደ ነው
የኮካ ኮላ ኩባንያ ከፊፋ የዓለም ዋንጫ ጋር የዘለቀውን የግማሽ ክፍለ ዘመን ታሪካዊ አጋርነት ለመዘከርና የዘንድሮውን 23ኛውን ዓለም አቀፍ የእግር ኳስ ውድድር መጀመር ለማብሰር ያዘጋጀው ልዩ የክብር ምሽት በአዲስ አበባ ስካይላይት ሆቴል በመካሄድ ላይ ይገኛል።
ይህ ታላቅ መርሃ ግብር በዓለም ዙሪያ የሚገኙ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ የስፖርት አፍቃሪዎች የውድድሩን መክፈቻ ስነ ስርዓትና የመጀመሪያ ጨዋታ ለመታደም በአንድነት ከሚሰበሰቡበት ታሪካዊ ቅጽበት ጋር ተስማሚ በሆነ መልኩ እየተከናወነ ነው።
በዚህ ማራኪ ድባብ ባለው መድረክ ላይ በርካታ ታዋቂ ሰዎች፣ የኪነጥበብ ባለሙያዎች፣ የስፖርት ቤተሰቦችና ጋዜጠኞች ተገኝተው ምሽቱን በልዩ የሙዚቃ ዝግጅቶች፣ የፈጠራ ስራዎችና የተለያዩ መዝናኛዎች እያደመቁት ይገኛሉ።
በመርሐግብሩ ላይ ንግግር ያደረጉት የኮካ ኮላ ሲኒየር ማርኬቲንግ ማናጀር ሜሮን ብርሃኑ እግር ኳስ ከስፖርትነቱ ባለፈ ሰዎችን በጋራ ስሜትና ፍቅር የሚያስተሳስር ሁለንተናዊ ቋንቋ መሆኑን ገልጸዋል።
የ2026ቱ የፊፋ የዓለም ዋንጫ በታሪክ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ሀገራትና ጨዋታዎች የሚስተናገዱበት ግዙፍ ውድድር መሆኑን የጠቆሙት ማናጀሯ፣ ኮካ ኮላ ትርጉም ባላቸው አቀራረቦች የኢትዮጵያን እግር ኳስ አፍቃሪዎች ከውድድሩ ደስታ ጋር ይበልጥ ለማገናኘት ቁርጠኛ መሆኑን አብራርተዋል።
በሌላ በኩል የኮካ ኮላ ቢቨሬጅስ አፍሪካ ተወካይ በበኩላቸው ኩባንያው በኢትዮጵያ ስላለው ጠንካራ ተሳትፎና ምርት ስርጭት ማብራሪያ ሰጥተዋል።
በአሁኑ ወቅት በሀገሪቱ አምስት ፋብሪካዎች እንደሚንቀሳቀሱና ከእነዚህም ውስጥ በአዲስ አበባ፣ ሰበታ፣ ባሕር ዳር እንዲሁም በድሬዳዋ የሚገኙት አራቱ ፋብሪካዎች የኮካ ኮላ ምርቶችን በሙሉ አቅማቸው እያመረቱ ለገበያ እያቀረቡ እንደሚገኝ አስታውቀዋል።
ከማሸጊያ ጋር በተያያዘም ለተለያዩ የደንበኞች ፍላጎት ተስማሚ የሆኑ ከ300 ሚሊ ሊትር ተመላሽ የብርጭቆ ጠርሙስ ጀምሮ ለጉዞ የሚመቹ የ350 እና የ500 ሚሊ ሊትር እንዲሁም ለቤተሰብና ለስብሰባዎች የሚሆኑ የ1.5 ሊትር የፒኢቲ ማሸጊያዎችን እያቀረቡ መሆኑን አስረድተዋል።
የዓለም ዋንጫውን ታላቅ ስሜትና የኮካ ኮላን ደማቅ ድባብ በቀጥታ ወደ እናንተ ማድረሳችንን እንቀጥላለን።
ውጤት
60" ሜክሲኮ 1 - 0 ደቡብ አፍሪካ
#worldcup #cocacola #football #skylighthotel #fifaworldcup #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
2 months ago
የኢትዮጵያና የማላዊ ብሔራዊ ቡድኖች ጨዋታቸውን በአንድ አቻ ውጤት አጠናቀቁ
#ethiopia | የኢትዮጵያ ብሔራዊ እግር ኳስ ቡድን ዛሬ ከማላዊ አቻው ጋር ባደረገው የወዳጅነት ግጥሚያ 1 ለ 1 በሆነ አቻ ውጤት ተለያይቷል።
በድሬዳዋ ስታዲየም ምሽት 12:00 ሰዓት ላይ በተጀመረው በዚህ ጨዋታ ለዋልያዎቹ ብቸኛዋን ግብ ቢኒያም በላይ ከመረብ ማገናኘት የቻለ ሲሆን የማላዊን የአቻነት ግብ ደግሞ አዴፖጁ ባባቱንዴ አስቆጥሯል።
በዋና አሰልጣኝ ዮሀንስ ሳህሌ የሚመራው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ባሳለፍነው ቅዳሜ በተመሳሳይ በድሬዳዋ ስታዲየም ከማላዊ ጋር ባደረገው የመጀመሪያ የወዳጅነት ጨዋታ 1 ለ 0 በሆነ ውጤት ማሸነፉ ይታወሳል።
#walyas #football #diredawa #ethiopianfootball #malawi #friendlymatch #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | የኢትዮጵያ ብሔራዊ እግር ኳስ ቡድን ዛሬ ከማላዊ አቻው ጋር ባደረገው የወዳጅነት ግጥሚያ 1 ለ 1 በሆነ አቻ ውጤት ተለያይቷል።
በድሬዳዋ ስታዲየም ምሽት 12:00 ሰዓት ላይ በተጀመረው በዚህ ጨዋታ ለዋልያዎቹ ብቸኛዋን ግብ ቢኒያም በላይ ከመረብ ማገናኘት የቻለ ሲሆን የማላዊን የአቻነት ግብ ደግሞ አዴፖጁ ባባቱንዴ አስቆጥሯል።
በዋና አሰልጣኝ ዮሀንስ ሳህሌ የሚመራው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ባሳለፍነው ቅዳሜ በተመሳሳይ በድሬዳዋ ስታዲየም ከማላዊ ጋር ባደረገው የመጀመሪያ የወዳጅነት ጨዋታ 1 ለ 0 በሆነ ውጤት ማሸነፉ ይታወሳል።
#walyas #football #diredawa #ethiopianfootball #malawi #friendlymatch #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
Comments