9 hours ago
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ የ2018 ዓ.ም የጾመ ፍልሰታን አስመልክተው አባታዊ መልዕክት አስተላለፉ
***********************
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ፣ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት ነገ ነሐሴ 1 ቀን የሚጀመረውን የ2018 ዓ.ም የጾመ ፍልሰታ ሱባኤን አስመልክተው ለመላው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ምዕመናን አባታዊ መልዕክት አስተላልፈዋል።
ቅዱስነታቸው ባስተላለፉት መልዕክት፣ እግዚአብሔርን መውደድ በተግባር የሚገለጸው ትእዛዙን በመጠበቅና የሰው ልጅን በሙሉ እንደ ራስ አድርጎ በመውደድ መሆኑን አስገንዝበዋል።
ለ15 ቀናት የሚጾመው የጾመ ማርያም (ፍልሰታ) መነሻ ምክንያትም የእግዚአብሔር ትዕዛዝ እና ፍቅር መሆኑን በመጠቆም፣ አምላክ የመረጣትን እና ከፍጥረታት ሁሉ አልቆ ያከበራትን ድንግል ማርያምን ማክበር አምላካዊ ትዕዛዝን መጠበቅ መሆኑን አብራርተዋል።
በመሆኑም ምዕመናን ይህንን የሱባኤ ወቅት የተራቡትን በመመገብ፣ የታረዙትን በማልበስ፣ የተጣሉትን በማስታረቅ፣ የታመሙትን እና የታሰሩትን በመጠየቅ፣ እንዲሁም ለኃጢአት የንስሐ ሥርየትን በመለመን እና ቅዱስ ቁርባን በመቀበል ሊያሳልፉት እንደሚገባ አባታዊ ጥሪያቸውን አቅርበዋል።
በሀገራችንም ሆነ በዓለም ዙሪያ ከፍተኛ ስጋት የሆነውን የፍጥረት አውዳሚ ጦርነት እግዚአብሔር በመለኮታዊ ጥበቡ እና ሥልጣኑ እንዲያስቆም፣ ምዕመናን በቅን ልቦና እና በትሑት ሰብእና ሆነው በሱባኤያቸው በጸሎት እንዲጠይቁ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ አደራ ብለዋል።
#ethiopia #ebc #religion #filseta
***********************
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ፣ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት ነገ ነሐሴ 1 ቀን የሚጀመረውን የ2018 ዓ.ም የጾመ ፍልሰታ ሱባኤን አስመልክተው ለመላው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ምዕመናን አባታዊ መልዕክት አስተላልፈዋል።
ቅዱስነታቸው ባስተላለፉት መልዕክት፣ እግዚአብሔርን መውደድ በተግባር የሚገለጸው ትእዛዙን በመጠበቅና የሰው ልጅን በሙሉ እንደ ራስ አድርጎ በመውደድ መሆኑን አስገንዝበዋል።
ለ15 ቀናት የሚጾመው የጾመ ማርያም (ፍልሰታ) መነሻ ምክንያትም የእግዚአብሔር ትዕዛዝ እና ፍቅር መሆኑን በመጠቆም፣ አምላክ የመረጣትን እና ከፍጥረታት ሁሉ አልቆ ያከበራትን ድንግል ማርያምን ማክበር አምላካዊ ትዕዛዝን መጠበቅ መሆኑን አብራርተዋል።
በመሆኑም ምዕመናን ይህንን የሱባኤ ወቅት የተራቡትን በመመገብ፣ የታረዙትን በማልበስ፣ የተጣሉትን በማስታረቅ፣ የታመሙትን እና የታሰሩትን በመጠየቅ፣ እንዲሁም ለኃጢአት የንስሐ ሥርየትን በመለመን እና ቅዱስ ቁርባን በመቀበል ሊያሳልፉት እንደሚገባ አባታዊ ጥሪያቸውን አቅርበዋል።
በሀገራችንም ሆነ በዓለም ዙሪያ ከፍተኛ ስጋት የሆነውን የፍጥረት አውዳሚ ጦርነት እግዚአብሔር በመለኮታዊ ጥበቡ እና ሥልጣኑ እንዲያስቆም፣ ምዕመናን በቅን ልቦና እና በትሑት ሰብእና ሆነው በሱባኤያቸው በጸሎት እንዲጠይቁ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ አደራ ብለዋል።
#ethiopia #ebc #religion #filseta
13 hours ago
“መልእክተ ቅዱስ ፓትርያርክ"
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሓዱ አምላክ፣ አሜን !
በሀገር ውስጥና በመላው ዓለም የምትገኙ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን እምነት ተከታዮች በሙሉ!
የሰውን ወገን ለማዳን የልጁ ማደሪያ ትሆን ዘንድ ድንግል ማርያምን የመረጠ መፍቀሬ ሰብእ እግዚአብሔር ኣምላካችን እንኳን ለሁለት ሺሕ ዓሥራ ስምንት ዓመተ ምሕረት ጾመ ማርያም ኣደረሰን ኣደረሳችሁ!
“ወእመሰ ታፈቅሩኒ ዕቀቡ ትእዛዝየ፡- ከወደዳችሁኝስ ትእዛዜን ጠብቁ" (ዮሐ.14፥15)፤
ፍቅር የሕያዋን ኣካላት ረቂቅ መገናኛ ነው፣ ሕያዋን ኣካላት በውጫዊው ግዙፍ ኣካላቸው በተወሰኑ ጊዜያትና ቦታ ይገናኛሉ ፤ ስለ ጋራ ጉዳያቸውም በጋራ ይመክራሉ፤ ይበልጥም ይቀራረባሉ፡፡
ይሁንና የሕያዋን ኣካላት ግንኙነት በኣካል በጊዜና በቦታ ብቻ የተወሰነ ኣይደለም፣ በፍቅረ መንፈስ ተገናኝተውም ይግባባሉ፣ ከኣካላዊ ግንኙነት በላይ የበለጠም ይኸው ፍቅረ መንፈስ ነው፤ ከዚህ ኣንጻር እግዚአብሔርንም ማግኘት የምንችለው በዚሁ ፍቅረ መንፈስ ሆነን በእምነት ዓይን ነው!
ይህም በመሆኑ ሓዋርያው ቅዱስ ዮሓንስ በመልእክቱ “በፍቅር የሚኖር በእግዚአብሔርይኖራል፣ እግዚአብሔርም በእርሱ ይኖራል" በማለት ያስተምረናል፣ (1ዮሐ. 4፥16) ይህም ማለት ከሱ ጋር በፍቅር ስንገናኝ፤ እሱም በኛ፣ እኛም በእሱ የመኖሩ ኩነት ይፈጠራል ማለት ነው፡፡
የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ምእመናንና ምእመናት!
ጌታችን “አፍቅሮ ለእግዚአብሔር ኣምላክከ፤- አምላክህን እግዚአብሔርን ውደደው" በማለት በፍጹም ልባችን እንድንወደው፣ እንደዚሁም ራሳችንን በምንወድበት መጠን እርስ በእርሳችን እንድንዋደድ ማዘዙን እናውቃለን፤
የመውደዳችን መለኪያ ሚዛንና መገለጫ ምልክትም ትእዛዙን ማክበርና መጠበቅ እንደሆነ “ብትወዱኝስ ትእዛዜን ጠብቁ” በማለት ኣስተምሮናል
ከዚህ ኣኳያ ጌታን መውደድ ማለት ትእዛዙን በመጠበቅ የሚገለጽ ግዙፍ ነገር እንጂ ምናባዊና የማይታይ ድብብቆሽ ነገር ኣይደለም ማለት ነው፣
ጌታችንን የመውደድ ነገር ትእዛዙን በመጠበቅ የሚገለጽ ከሆነ ትእዛዙ ምንድን ነው? የሚለውን ማየት ኣስፈላጊ ይሆናል፤ ትእዛዙን በጥቅል ስናይ እግዚአብሔርንና ባልንጀራን በመውደድ እንደሚጠቃለል ራሱ ጌታችን ኣስገንዝቦናል፣
በተለይም በባልንጀራችን ላይ የምንከተለው መውደድ ከላይ እንደተገለጸው “እንደራስህ ኣድርገህ ውደድ" ተብለ በግልጽ ተቀምጦኣል፤
የሰው ባልንጀራ እነማን ናቸው? በሕይወት ያሉት ናቸው? ወይስ የሞቱት? ወገን ዘመድ? ወይስ የሰው ወገን በሙሉ የሚለውንም ማወቅ ኣስፈላጊ ነው፡፡
ጌታችን ነገሩን በዚህ ደረጃ ለያይቶ ኣላስቀመጠም፣ ለምን? ቢባል ባልንጀራ ማለት የተወሰነን የማኅበረ ሰብ ወገን የሚያሳይ ሳይሆን መላውን የሰው ወገን የሚገልጽ በመሆኑ፤ እንደዚሁም የሞቱም ሆኑ ያለነው ሁላችን በእሱ ፊት ሕያዋንና እርስ በእርሳችን ባልንጀሮች በመሆናችን ነው፤
በመሆኑም መዋደዳችንም ሆነ መከባበራችን በሕይወተ ሥጋ ሳለን ብቻ ሳይሆን ከዚያም በኋላ እስከ በሌለው ዕድሜ በመሆኑ ጌታችን በጊዜ በቦታና በከፊል ለይቶ ኣላስቀመጠም፡፡
የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ምእመናንና ምእመናት !
ከነሐሴ ፩ ቀን ጀምሮ ለ፲፭ ቀናት የምንጾመው የጾመ ማርያም መነሻ ምክንያቱ የእግዚአብሔርትእዛዝና ፍቅር ነው፣
እግዚአብሔር ሰውን በኣጠቃላይ በተለይም ደግሞ እንደፈቃዱ የኖሩ ቅዱሳንን እንድናከብርኣዞናል ክቅዱሳን ፍጥረታት መካክል ደግሞ ቅድስት ድንግል ማርያም የመጀመሪያውን ደረጃ ትይዛለች፤
ይህም በመሆኑ ከፍጥረት ወገን ከሏ ክብር የሚደርስ ባለመኖሩ ከሁሉም ኣብልጠን እናክብራታለን፤
ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በዚህ ደረጃ የድንግል ማርያምን ክብር ስትገልጽ ክእግዚአብሔርና ለባስያነ እግዚአብሔር ክሆኑ ቀደምት ኣበው ተምራ ነው!
በአራተኛው መቶ ክፍለ ዘመን የነበረው ዕውቁ ቅዱስና ዓለም ዓቀፋዊው አባት ቅዱስ ኤፍሬም የድንግል ማርያምን ክብር! ቅድስና እና ልዕልና ሲናገር “ይእቲ ተዓቢ እምኪሩቤል፡ ወትፈደፍድ እምሱራፌል፣ እስመ ኮነት ታቦተ ለአሓዱ ዘእምቅድስት ሥላሴ- እሷ ከኪሩቤል ትበልጣለች! ከሱራፌልም ትልቃለች፣ ከቅድስት ሥላሴ ኣንዱ ለሆነው ታቦት ወይም ማደሪያ ሆናለችና" በማለት አስተምሮናል፡፡
በመሆኑም ለስሟ መታሰቢያ በሆነው በዚህ ጾም ድንግል ማርያምን በዚህ ደረጃ ስናክብርትእዛዙን እንጠብቃለን፤ ትእዛዙን በመጠበቃችን ደግሞ እሱን መውደዳችንን እናረጋግጣለን ! እኛ ድንግል ማርያምን እንድንወዳት "እናታችሁ'' ብሎ እንዳዘዘ፣ እሷም ልትወደን “ልጆችዅ ተብላ ታዛለችና ስለኛ ትጸልያለች፡፡
በጸሎቷም ከመከራ ትታደገናለች፤ በኣጠቃላይ በእግዚአብሔር' በቅዱሳንና በእኛ መካከል ያለው ግንኙነት በዚህ ትእዛዝና ፍቅር በትዕይንተ ዓለም ባለች ቤተ ክርስቲያን ዘንድ የተሳሰረ ነው፡፡
ስለሆነም በዚህ የጾመ ፍልሰታ ለማርያም ሱባዔ የተራቡትን በመመገብ፣ የታረዙትን በማልበስ፣ የተጣሎትን በማስታረቅ፤ የታመሙትንና የታስሩትን በመጠየቅ፤ ቅዱስ ቍርባንን በመቀበልና ለኃጢኣታችን የንሥሐ ሥርየትን በመለመን ሱባዔውን ልናሳልፍ ይገባል፡፡
በመጨረሻም
በሀገራችንም ሆነ በዓለም ዙሪያ ከባድ ስጋት የሆነው የፍጥረት ኣውዳሚ ጦርነትን በመለኮታዊ ጥበቡና ሥልጣኑ እንዲያስቆምልን በቅን ልቡና፤ በትሑት ሰብእና ሆነን እግዚአብሔርን በዚህ ሱባዔ እንድንጠይቀው ኣደራ ጭምር ኣባታዊ መልክታችንን በእግዚአብሔር ስም እናስተላልፋለን፤
የተባረከና የተቀደስ ጾም ያድርግልን፤
እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ሕዝቦችዋን ይባርክ!
ወስብሐት ለእግዚአብሔር፣ አሜን!
አባ ማትያስ ቀዳማዊ
ፓትርያርክ ርእስ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ
ሊቀ ጳጳስ ዘኣኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት
ነሐሴ 1 ቀን 2018 ዓ.ም
አዲስ አበባ፤ ኢትዮጵያ
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሓዱ አምላክ፣ አሜን !
በሀገር ውስጥና በመላው ዓለም የምትገኙ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን እምነት ተከታዮች በሙሉ!
የሰውን ወገን ለማዳን የልጁ ማደሪያ ትሆን ዘንድ ድንግል ማርያምን የመረጠ መፍቀሬ ሰብእ እግዚአብሔር ኣምላካችን እንኳን ለሁለት ሺሕ ዓሥራ ስምንት ዓመተ ምሕረት ጾመ ማርያም ኣደረሰን ኣደረሳችሁ!
“ወእመሰ ታፈቅሩኒ ዕቀቡ ትእዛዝየ፡- ከወደዳችሁኝስ ትእዛዜን ጠብቁ" (ዮሐ.14፥15)፤
ፍቅር የሕያዋን ኣካላት ረቂቅ መገናኛ ነው፣ ሕያዋን ኣካላት በውጫዊው ግዙፍ ኣካላቸው በተወሰኑ ጊዜያትና ቦታ ይገናኛሉ ፤ ስለ ጋራ ጉዳያቸውም በጋራ ይመክራሉ፤ ይበልጥም ይቀራረባሉ፡፡
ይሁንና የሕያዋን ኣካላት ግንኙነት በኣካል በጊዜና በቦታ ብቻ የተወሰነ ኣይደለም፣ በፍቅረ መንፈስ ተገናኝተውም ይግባባሉ፣ ከኣካላዊ ግንኙነት በላይ የበለጠም ይኸው ፍቅረ መንፈስ ነው፤ ከዚህ ኣንጻር እግዚአብሔርንም ማግኘት የምንችለው በዚሁ ፍቅረ መንፈስ ሆነን በእምነት ዓይን ነው!
ይህም በመሆኑ ሓዋርያው ቅዱስ ዮሓንስ በመልእክቱ “በፍቅር የሚኖር በእግዚአብሔርይኖራል፣ እግዚአብሔርም በእርሱ ይኖራል" በማለት ያስተምረናል፣ (1ዮሐ. 4፥16) ይህም ማለት ከሱ ጋር በፍቅር ስንገናኝ፤ እሱም በኛ፣ እኛም በእሱ የመኖሩ ኩነት ይፈጠራል ማለት ነው፡፡
የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ምእመናንና ምእመናት!
ጌታችን “አፍቅሮ ለእግዚአብሔር ኣምላክከ፤- አምላክህን እግዚአብሔርን ውደደው" በማለት በፍጹም ልባችን እንድንወደው፣ እንደዚሁም ራሳችንን በምንወድበት መጠን እርስ በእርሳችን እንድንዋደድ ማዘዙን እናውቃለን፤
የመውደዳችን መለኪያ ሚዛንና መገለጫ ምልክትም ትእዛዙን ማክበርና መጠበቅ እንደሆነ “ብትወዱኝስ ትእዛዜን ጠብቁ” በማለት ኣስተምሮናል
ከዚህ ኣኳያ ጌታን መውደድ ማለት ትእዛዙን በመጠበቅ የሚገለጽ ግዙፍ ነገር እንጂ ምናባዊና የማይታይ ድብብቆሽ ነገር ኣይደለም ማለት ነው፣
ጌታችንን የመውደድ ነገር ትእዛዙን በመጠበቅ የሚገለጽ ከሆነ ትእዛዙ ምንድን ነው? የሚለውን ማየት ኣስፈላጊ ይሆናል፤ ትእዛዙን በጥቅል ስናይ እግዚአብሔርንና ባልንጀራን በመውደድ እንደሚጠቃለል ራሱ ጌታችን ኣስገንዝቦናል፣
በተለይም በባልንጀራችን ላይ የምንከተለው መውደድ ከላይ እንደተገለጸው “እንደራስህ ኣድርገህ ውደድ" ተብለ በግልጽ ተቀምጦኣል፤
የሰው ባልንጀራ እነማን ናቸው? በሕይወት ያሉት ናቸው? ወይስ የሞቱት? ወገን ዘመድ? ወይስ የሰው ወገን በሙሉ የሚለውንም ማወቅ ኣስፈላጊ ነው፡፡
ጌታችን ነገሩን በዚህ ደረጃ ለያይቶ ኣላስቀመጠም፣ ለምን? ቢባል ባልንጀራ ማለት የተወሰነን የማኅበረ ሰብ ወገን የሚያሳይ ሳይሆን መላውን የሰው ወገን የሚገልጽ በመሆኑ፤ እንደዚሁም የሞቱም ሆኑ ያለነው ሁላችን በእሱ ፊት ሕያዋንና እርስ በእርሳችን ባልንጀሮች በመሆናችን ነው፤
በመሆኑም መዋደዳችንም ሆነ መከባበራችን በሕይወተ ሥጋ ሳለን ብቻ ሳይሆን ከዚያም በኋላ እስከ በሌለው ዕድሜ በመሆኑ ጌታችን በጊዜ በቦታና በከፊል ለይቶ ኣላስቀመጠም፡፡
የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ምእመናንና ምእመናት !
ከነሐሴ ፩ ቀን ጀምሮ ለ፲፭ ቀናት የምንጾመው የጾመ ማርያም መነሻ ምክንያቱ የእግዚአብሔርትእዛዝና ፍቅር ነው፣
እግዚአብሔር ሰውን በኣጠቃላይ በተለይም ደግሞ እንደፈቃዱ የኖሩ ቅዱሳንን እንድናከብርኣዞናል ክቅዱሳን ፍጥረታት መካክል ደግሞ ቅድስት ድንግል ማርያም የመጀመሪያውን ደረጃ ትይዛለች፤
ይህም በመሆኑ ከፍጥረት ወገን ከሏ ክብር የሚደርስ ባለመኖሩ ከሁሉም ኣብልጠን እናክብራታለን፤
ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በዚህ ደረጃ የድንግል ማርያምን ክብር ስትገልጽ ክእግዚአብሔርና ለባስያነ እግዚአብሔር ክሆኑ ቀደምት ኣበው ተምራ ነው!
በአራተኛው መቶ ክፍለ ዘመን የነበረው ዕውቁ ቅዱስና ዓለም ዓቀፋዊው አባት ቅዱስ ኤፍሬም የድንግል ማርያምን ክብር! ቅድስና እና ልዕልና ሲናገር “ይእቲ ተዓቢ እምኪሩቤል፡ ወትፈደፍድ እምሱራፌል፣ እስመ ኮነት ታቦተ ለአሓዱ ዘእምቅድስት ሥላሴ- እሷ ከኪሩቤል ትበልጣለች! ከሱራፌልም ትልቃለች፣ ከቅድስት ሥላሴ ኣንዱ ለሆነው ታቦት ወይም ማደሪያ ሆናለችና" በማለት አስተምሮናል፡፡
በመሆኑም ለስሟ መታሰቢያ በሆነው በዚህ ጾም ድንግል ማርያምን በዚህ ደረጃ ስናክብርትእዛዙን እንጠብቃለን፤ ትእዛዙን በመጠበቃችን ደግሞ እሱን መውደዳችንን እናረጋግጣለን ! እኛ ድንግል ማርያምን እንድንወዳት "እናታችሁ'' ብሎ እንዳዘዘ፣ እሷም ልትወደን “ልጆችዅ ተብላ ታዛለችና ስለኛ ትጸልያለች፡፡
በጸሎቷም ከመከራ ትታደገናለች፤ በኣጠቃላይ በእግዚአብሔር' በቅዱሳንና በእኛ መካከል ያለው ግንኙነት በዚህ ትእዛዝና ፍቅር በትዕይንተ ዓለም ባለች ቤተ ክርስቲያን ዘንድ የተሳሰረ ነው፡፡
ስለሆነም በዚህ የጾመ ፍልሰታ ለማርያም ሱባዔ የተራቡትን በመመገብ፣ የታረዙትን በማልበስ፣ የተጣሎትን በማስታረቅ፤ የታመሙትንና የታስሩትን በመጠየቅ፤ ቅዱስ ቍርባንን በመቀበልና ለኃጢኣታችን የንሥሐ ሥርየትን በመለመን ሱባዔውን ልናሳልፍ ይገባል፡፡
በመጨረሻም
በሀገራችንም ሆነ በዓለም ዙሪያ ከባድ ስጋት የሆነው የፍጥረት ኣውዳሚ ጦርነትን በመለኮታዊ ጥበቡና ሥልጣኑ እንዲያስቆምልን በቅን ልቡና፤ በትሑት ሰብእና ሆነን እግዚአብሔርን በዚህ ሱባዔ እንድንጠይቀው ኣደራ ጭምር ኣባታዊ መልክታችንን በእግዚአብሔር ስም እናስተላልፋለን፤
የተባረከና የተቀደስ ጾም ያድርግልን፤
እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ሕዝቦችዋን ይባርክ!
ወስብሐት ለእግዚአብሔር፣ አሜን!
አባ ማትያስ ቀዳማዊ
ፓትርያርክ ርእስ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ
ሊቀ ጳጳስ ዘኣኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት
ነሐሴ 1 ቀን 2018 ዓ.ም
አዲስ አበባ፤ ኢትዮጵያ
14 hours ago
“መልእክተ ቅዱስ ፓትርያርክ"
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሓዱ አምላክ፣ አሜን !
በሀገር ውስጥና በመላው ዓለም የምትገኙ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን እምነት ተከታዮች በሙሉ!
የሰውን ወገን ለማዳን የልጁ ማደሪያ ትሆን ዘንድ ድንግል ማርያምን የመረጠ መፍቀሬ ሰብእ እግዚአብሔር ኣምላካችን እንኳን ለሁለት ሺሕ ዓሥራ ስምንት ዓመተ ምሕረት ጾመ ማርያም ኣደረሰን ኣደረሳችሁ!
“ወእመሰ ታፈቅሩኒ ዕቀቡ ትእዛዝየ፡- ከወደዳችሁኝስ ትእዛዜን ጠብቁ" (ዮሐ.14፥15)፤
ፍቅር የሕያዋን ኣካላት ረቂቅ መገናኛ ነው፣ ሕያዋን ኣካላት በውጫዊው ግዙፍ ኣካላቸው በተወሰኑ ጊዜያትና ቦታ ይገናኛሉ ፤ ስለ ጋራ ጉዳያቸውም በጋራ ይመክራሉ፤ ይበልጥም ይቀራረባሉ፡፡
ይሁንና የሕያዋን ኣካላት ግንኙነት በኣካል በጊዜና በቦታ ብቻ የተወሰነ ኣይደለም፣ በፍቅረ መንፈስ ተገናኝተውም ይግባባሉ፣ ከኣካላዊ ግንኙነት በላይ የበለጠም ይኸው ፍቅረ መንፈስ ነው፤ ከዚህ ኣንጻር እግዚአብሔርንም ማግኘት የምንችለው በዚሁ ፍቅረ መንፈስ ሆነን በእምነት ዓይን ነው!
ይህም በመሆኑ ሓዋርያው ቅዱስ ዮሓንስ በመልእክቱ “በፍቅር የሚኖር በእግዚአብሔርይኖራል፣ እግዚአብሔርም በእርሱ ይኖራል" በማለት ያስተምረናል፣ (1ዮሐ. 4፥16) ይህም ማለት ከሱ ጋር በፍቅር ስንገናኝ፤ እሱም በኛ፣ እኛም በእሱ የመኖሩ ኩነት ይፈጠራል ማለት ነው፡፡
የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ምእመናንና ምእመናት!
ጌታችን “አፍቅሮ ለእግዚአብሔር ኣምላክከ፤- አምላክህን እግዚአብሔርን ውደደው" በማለት በፍጹም ልባችን እንድንወደው፣ እንደዚሁም ራሳችንን በምንወድበት መጠን እርስ በእርሳችን እንድንዋደድ ማዘዙን እናውቃለን፤
የመውደዳችን መለኪያ ሚዛንና መገለጫ ምልክትም ትእዛዙን ማክበርና መጠበቅ እንደሆነ “ብትወዱኝስ ትእዛዜን ጠብቁ” በማለት ኣስተምሮናል ከዚህ ኣኳያ ጌታን መውደድ ማለት ትእዛዙን በመጠበቅ የሚገለጽ ግዙፍ ነገር እንጂ ምናባዊና የማይታይ ድብብቆሽ ነገር ኣይደለም ማለት ነው፣
ጌታችንን የመውደድ ነገር ትእዛዙን በመጠበቅ የሚገለጽ ከሆነ ትእዛዙ ምንድን ነው? የሚለውን ማየት ኣስፈላጊ ይሆናል፤ ትእዛዙን በጥቅል ስናይ እግዚአብሔርንና ባልንጀራን በመውደድ እንደሚጠቃለል ራሱ ጌታችን ኣስገንዝቦናል፣
በተለይም በባልንጀራችን ላይ የምንከተለው መውደድ ከላይ እንደተገለጸው “እንደራስህ ኣድርገህ ውደድ" ተብለ በግልጽ ተቀምጦኣል፤ የሰው ባልንጀራ እነማን ናቸው? በሕይወት ያሉት ናቸው? ወይስ የሞቱት? ወገን ዘመድ? ወይስ የሰው ወገን በሙሉ የሚለውንም ማወቅ ኣስፈላጊ ነው፡፡
ጌታችን ነገሩን በዚህ ደረጃ ለያይቶ ኣላስቀመጠም፣ ለምን? ቢባል ባልንጀራ ማለት የተወሰነን የማኅበረ ሰብ ወገን የሚያሳይ ሳይሆን መላውን የሰው ወገን የሚገልጽ በመሆኑ፤ እንደዚሁም የሞቱም ሆኑ ያለነው ሁላችን በእሱ ፊት ሕያዋንና እርስ በእርሳችን ባልንጀሮች በመሆናችን ነው፤
በመሆኑም መዋደዳችንም ሆነ መከባበራችን በሕይወተ ሥጋ ሳለን ብቻ ሳይሆን ከዚያም በኋላ እስከ በሌለው ዕድሜ በመሆኑ ጌታችን በጊዜ በቦታና በከፊል ለይቶ ኣላስቀመጠም፡፡
የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ምእመናንና ምእመናት !
ከነሐሴ ፩ ቀን ጀምሮ ለ፲፭ ቀናት የምንጾመው የጾመ ማርያም መነሻ ምክንያቱ የእግዚአብሔርትእዛዝና ፍቅር ነው፣
እግዚአብሔር ሰውን በኣጠቃላይ በተለይም ደግሞ እንደፈቃዱ የኖሩ ቅዱሳንን እንድናከብርኣዞናል ክቅዱሳን ፍጥረታት መካክል ደግሞ ቅድስት ድንግል ማርያም የመጀመሪያውን ደረጃ ትይዛለች፤
ይህም በመሆኑ ከፍጥረት ወገን ከሏ ክብር የሚደርስ ባለመኖሩ ከሁሉም ኣብልጠን እናክብራታለን፤
ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በዚህ ደረጃ የድንግል ማርያምን ክብር ስትገልጽ ክእግዚአብሔርና ለባስያነ እግዚአብሔር ክሆኑ ቀደምት ኣበው ተምራ ነው!
በአራተኛው መቶ ክፍለ ዘመን የነበረው ዕውቁ ቅዱስና ዓለም ዓቀፋዊው አባት ቅዱስ ኤፍሬም የድንግል ማርያምን ክብር! ቅድስና እና ልዕልና ሲናገር “ይእቲ ተዓቢ እምኪሩቤል፡ ወትፈደፍድ እምሱራፌል፣ እስመ ኮነት ታቦተ ለአሓዱ ዘእምቅድስት ሥላሴ- እሷ ከኪሩቤል ትበልጣለች! ከሱራፌልም ትልቃለች፣ ከቅድስት ሥላሴ ኣንዱ ለሆነው ታቦት ወይም ማደሪያ ሆናለችና" በማለት አስተምሮናል፡፡
በመሆኑም ለስሟ መታሰቢያ በሆነው በዚህ ጾም ድንግል ማርያምን በዚህ ደረጃ ስናክብርትእዛዙን እንጠብቃለን፤ ትእዛዙን በመጠበቃችን ደግሞ እሱን መውደዳችንን እናረጋግጣለን ! እኛ ድንግል ማርያምን እንድንወዳት "እናታችሁ'' ብሎ እንዳዘዘ፣ እሷም ልትወደን “ልጆችዅ ተብላ ታዛለችና ስለኛ ትጸልያለች፡፡
በጸሎቷም ከመከራ ትታደገናለች፤ በኣጠቃላይ በእግዚአብሔር' በቅዱሳንና በእኛ መካከል ያለው ግንኙነት በዚህ ትእዛዝና ፍቅር በትዕይንተ ዓለም ባለች ቤተ ክርስቲያን ዘንድ የተሳሰረ ነው፡፡
ስለሆነም በዚህ የጾመ ፍልሰታ ለማርያም ሱባዔ የተራቡትን በመመገብ፣ የታረዙትን በማልበስ፣ የተጣሎትን በማስታረቅ፤ የታመሙትንና የታስሩትን በመጠየቅ፤ ቅዱስ ቍርባንን በመቀበልና ለኃጢኣታችን የንሥሐ ሥርየትን በመለመን ሱባዔውን ልናሳልፍ ይገባል፡፡
በመጨረሻም
በሀገራችንም ሆነ በዓለም ዙሪያ ከባድ ስጋት የሆነው የፍጥረት ኣውዳሚ ጦርነትን በመለኮታዊ ጥበቡና ሥልጣኑ እንዲያስቆምልን በቅን ልቡና፤ በትሑት ሰብእና ሆነን እግዚአብሔርን በዚህ ሱባዔ እንድንጠይቀው ኣደራ ጭምር ኣባታዊ መልክታችንን በእግዚአብሔር ስም እናስተላልፋለን፤
የተባረከና የተቀደስ ጾም ያድርግልን፤
እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ሕዝቦችዋን ይባርክ!
ወስብሐት ለእግዚአብሔር፣ አሜን!
አባ ማትያስ ቀዳማዊ
ፓትርያርክ ርእስ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ
ሊቀ ጳጳስ ዘኣኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት
ነሐሴ 1 ቀን 2018 ዓ.ም
አዲስ አበባ፤ ኢትዮጵያ
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሓዱ አምላክ፣ አሜን !
በሀገር ውስጥና በመላው ዓለም የምትገኙ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን እምነት ተከታዮች በሙሉ!
የሰውን ወገን ለማዳን የልጁ ማደሪያ ትሆን ዘንድ ድንግል ማርያምን የመረጠ መፍቀሬ ሰብእ እግዚአብሔር ኣምላካችን እንኳን ለሁለት ሺሕ ዓሥራ ስምንት ዓመተ ምሕረት ጾመ ማርያም ኣደረሰን ኣደረሳችሁ!
“ወእመሰ ታፈቅሩኒ ዕቀቡ ትእዛዝየ፡- ከወደዳችሁኝስ ትእዛዜን ጠብቁ" (ዮሐ.14፥15)፤
ፍቅር የሕያዋን ኣካላት ረቂቅ መገናኛ ነው፣ ሕያዋን ኣካላት በውጫዊው ግዙፍ ኣካላቸው በተወሰኑ ጊዜያትና ቦታ ይገናኛሉ ፤ ስለ ጋራ ጉዳያቸውም በጋራ ይመክራሉ፤ ይበልጥም ይቀራረባሉ፡፡
ይሁንና የሕያዋን ኣካላት ግንኙነት በኣካል በጊዜና በቦታ ብቻ የተወሰነ ኣይደለም፣ በፍቅረ መንፈስ ተገናኝተውም ይግባባሉ፣ ከኣካላዊ ግንኙነት በላይ የበለጠም ይኸው ፍቅረ መንፈስ ነው፤ ከዚህ ኣንጻር እግዚአብሔርንም ማግኘት የምንችለው በዚሁ ፍቅረ መንፈስ ሆነን በእምነት ዓይን ነው!
ይህም በመሆኑ ሓዋርያው ቅዱስ ዮሓንስ በመልእክቱ “በፍቅር የሚኖር በእግዚአብሔርይኖራል፣ እግዚአብሔርም በእርሱ ይኖራል" በማለት ያስተምረናል፣ (1ዮሐ. 4፥16) ይህም ማለት ከሱ ጋር በፍቅር ስንገናኝ፤ እሱም በኛ፣ እኛም በእሱ የመኖሩ ኩነት ይፈጠራል ማለት ነው፡፡
የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ምእመናንና ምእመናት!
ጌታችን “አፍቅሮ ለእግዚአብሔር ኣምላክከ፤- አምላክህን እግዚአብሔርን ውደደው" በማለት በፍጹም ልባችን እንድንወደው፣ እንደዚሁም ራሳችንን በምንወድበት መጠን እርስ በእርሳችን እንድንዋደድ ማዘዙን እናውቃለን፤
የመውደዳችን መለኪያ ሚዛንና መገለጫ ምልክትም ትእዛዙን ማክበርና መጠበቅ እንደሆነ “ብትወዱኝስ ትእዛዜን ጠብቁ” በማለት ኣስተምሮናል ከዚህ ኣኳያ ጌታን መውደድ ማለት ትእዛዙን በመጠበቅ የሚገለጽ ግዙፍ ነገር እንጂ ምናባዊና የማይታይ ድብብቆሽ ነገር ኣይደለም ማለት ነው፣
ጌታችንን የመውደድ ነገር ትእዛዙን በመጠበቅ የሚገለጽ ከሆነ ትእዛዙ ምንድን ነው? የሚለውን ማየት ኣስፈላጊ ይሆናል፤ ትእዛዙን በጥቅል ስናይ እግዚአብሔርንና ባልንጀራን በመውደድ እንደሚጠቃለል ራሱ ጌታችን ኣስገንዝቦናል፣
በተለይም በባልንጀራችን ላይ የምንከተለው መውደድ ከላይ እንደተገለጸው “እንደራስህ ኣድርገህ ውደድ" ተብለ በግልጽ ተቀምጦኣል፤ የሰው ባልንጀራ እነማን ናቸው? በሕይወት ያሉት ናቸው? ወይስ የሞቱት? ወገን ዘመድ? ወይስ የሰው ወገን በሙሉ የሚለውንም ማወቅ ኣስፈላጊ ነው፡፡
ጌታችን ነገሩን በዚህ ደረጃ ለያይቶ ኣላስቀመጠም፣ ለምን? ቢባል ባልንጀራ ማለት የተወሰነን የማኅበረ ሰብ ወገን የሚያሳይ ሳይሆን መላውን የሰው ወገን የሚገልጽ በመሆኑ፤ እንደዚሁም የሞቱም ሆኑ ያለነው ሁላችን በእሱ ፊት ሕያዋንና እርስ በእርሳችን ባልንጀሮች በመሆናችን ነው፤
በመሆኑም መዋደዳችንም ሆነ መከባበራችን በሕይወተ ሥጋ ሳለን ብቻ ሳይሆን ከዚያም በኋላ እስከ በሌለው ዕድሜ በመሆኑ ጌታችን በጊዜ በቦታና በከፊል ለይቶ ኣላስቀመጠም፡፡
የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ምእመናንና ምእመናት !
ከነሐሴ ፩ ቀን ጀምሮ ለ፲፭ ቀናት የምንጾመው የጾመ ማርያም መነሻ ምክንያቱ የእግዚአብሔርትእዛዝና ፍቅር ነው፣
እግዚአብሔር ሰውን በኣጠቃላይ በተለይም ደግሞ እንደፈቃዱ የኖሩ ቅዱሳንን እንድናከብርኣዞናል ክቅዱሳን ፍጥረታት መካክል ደግሞ ቅድስት ድንግል ማርያም የመጀመሪያውን ደረጃ ትይዛለች፤
ይህም በመሆኑ ከፍጥረት ወገን ከሏ ክብር የሚደርስ ባለመኖሩ ከሁሉም ኣብልጠን እናክብራታለን፤
ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በዚህ ደረጃ የድንግል ማርያምን ክብር ስትገልጽ ክእግዚአብሔርና ለባስያነ እግዚአብሔር ክሆኑ ቀደምት ኣበው ተምራ ነው!
በአራተኛው መቶ ክፍለ ዘመን የነበረው ዕውቁ ቅዱስና ዓለም ዓቀፋዊው አባት ቅዱስ ኤፍሬም የድንግል ማርያምን ክብር! ቅድስና እና ልዕልና ሲናገር “ይእቲ ተዓቢ እምኪሩቤል፡ ወትፈደፍድ እምሱራፌል፣ እስመ ኮነት ታቦተ ለአሓዱ ዘእምቅድስት ሥላሴ- እሷ ከኪሩቤል ትበልጣለች! ከሱራፌልም ትልቃለች፣ ከቅድስት ሥላሴ ኣንዱ ለሆነው ታቦት ወይም ማደሪያ ሆናለችና" በማለት አስተምሮናል፡፡
በመሆኑም ለስሟ መታሰቢያ በሆነው በዚህ ጾም ድንግል ማርያምን በዚህ ደረጃ ስናክብርትእዛዙን እንጠብቃለን፤ ትእዛዙን በመጠበቃችን ደግሞ እሱን መውደዳችንን እናረጋግጣለን ! እኛ ድንግል ማርያምን እንድንወዳት "እናታችሁ'' ብሎ እንዳዘዘ፣ እሷም ልትወደን “ልጆችዅ ተብላ ታዛለችና ስለኛ ትጸልያለች፡፡
በጸሎቷም ከመከራ ትታደገናለች፤ በኣጠቃላይ በእግዚአብሔር' በቅዱሳንና በእኛ መካከል ያለው ግንኙነት በዚህ ትእዛዝና ፍቅር በትዕይንተ ዓለም ባለች ቤተ ክርስቲያን ዘንድ የተሳሰረ ነው፡፡
ስለሆነም በዚህ የጾመ ፍልሰታ ለማርያም ሱባዔ የተራቡትን በመመገብ፣ የታረዙትን በማልበስ፣ የተጣሎትን በማስታረቅ፤ የታመሙትንና የታስሩትን በመጠየቅ፤ ቅዱስ ቍርባንን በመቀበልና ለኃጢኣታችን የንሥሐ ሥርየትን በመለመን ሱባዔውን ልናሳልፍ ይገባል፡፡
በመጨረሻም
በሀገራችንም ሆነ በዓለም ዙሪያ ከባድ ስጋት የሆነው የፍጥረት ኣውዳሚ ጦርነትን በመለኮታዊ ጥበቡና ሥልጣኑ እንዲያስቆምልን በቅን ልቡና፤ በትሑት ሰብእና ሆነን እግዚአብሔርን በዚህ ሱባዔ እንድንጠይቀው ኣደራ ጭምር ኣባታዊ መልክታችንን በእግዚአብሔር ስም እናስተላልፋለን፤
የተባረከና የተቀደስ ጾም ያድርግልን፤
እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ሕዝቦችዋን ይባርክ!
ወስብሐት ለእግዚአብሔር፣ አሜን!
አባ ማትያስ ቀዳማዊ
ፓትርያርክ ርእስ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ
ሊቀ ጳጳስ ዘኣኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት
ነሐሴ 1 ቀን 2018 ዓ.ም
አዲስ አበባ፤ ኢትዮጵያ
3 days ago
የዘመናችን ሉዓላዊነት፡ ከድንበር ጥበቃ እስከ ኢኮኖሚያዊና ዲጂታል ልዕልና
*******************
( የዕለቱ መልዕክት)
ትናንት የሀገር ዳር ድንበር በጀግኖች ደምና አጥንት ይጠበቅ ነበር። ዛሬ ግን የዓለማችን የጂኦ-ፖለቲካ መልክ እና የኃይል አሰላለፍ መሰረታዊ ለውጥ ሲያስተናግድ፣ የሉዓላዊነት ትርጓሜም እጅግ ጥልቅ የሆነ አዲስ ገጽታን ተላብሷል።
በ21ኛው ክፍለ ዘመን የኢትዮጵያ ሉዓላዊነት እና የህልውና ዋስትና የሚረጋገጠው ጂኦግራፊያዊ ድንበርን በጦር መሣሪያ በመጠበቅ ብቻ ሳይሆን በስንዴ ማሳዎቻችን ስፋት፣ በፋብሪካዎቻችን የማምረት አቅም እንዲሁም በዲጂታል ቴክኖሎጂ ብቃታችን ጭምር ነው።
እውነተኛ ነፃነት ማለት የራስን ትርክት በራስ አቅም መጻፍ መቻል፣ የራስን ህዝብ በራስ አቅም መመገብ እና የሀገርን ጉዳይ ያለ አንዳች የውጭ ጫና መወሰን መቻል ማለት ነው።
ይህ ሉዓለዊነት ከእርዳታ ጥገኝነት እና ከተረጂነት አዘቅት ተላቆ በምግብ ራስን መቻልን፣ ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ አቅም ማምረትን እና በከንቱ የሚባክኑ የተፈጥሮ ጸጋዎቻችንን ወደ ሀገራዊ ሀብት መቀየርን ማዕከል ያደረገ ነው።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) "ደሃ አይከበርም፤ እየለመነ የሚኖር ሀገር አይከበርም" ሲሉ የተናገሩት መራር ሀቅ፣ የዘመናችንን የሉዓላዊነት ትግል ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ ነው። ክብራችን በዓለም አቀፍ መድረክ ላይ ደምቆ የሚታየው፣ ቃላችንም የሚሰማው ፖሊሲዎቻችንን ያለማንም ጣልቃ ገብነት ማስፈጸም የሚያስችል የኢኮኖሚ ጡንቻ ስንገነባ ብቻ መሆኑን ይህ አዲስ እሳቤ ያስገነዝበናል።
ይህ ሁለንተናዊ የኢኮኖሚ እና የቴክኖሎጂ ሉዓላዊነት እርስበርስ በተሳሰሩ ጠንካራ ምሰሶዎች ላይ የቆመ ነው። የግብርናው ዘርፍ ዜጎችን ከረሃብ ከመታደግ አልፎ፣ ሀገርን በእርዳታ ስም ከሚመጣ የፖለቲካ ተጽዕኖ እና የውጭ ጫና ነጻ የማውጣት አቅም አለው።
ከዚህ ጎን ለጎን አምራች ኢንዱስትሪውና ማዕድን ልማቱ የውጭ ምንዛሬን በማስገኘት ሀገራዊ ሜጋ ፕሮጀክቶቻችንን በራሳችን አቅም እንድንገነባና ኢኮኖሚያችን እንዲጠናከሩ እያደረጉ ይገኛሉ። የቱሪዝም ዘርፉ የብሔራዊ ገጽታችንን ከመገንባት ባሻገር ባህላችንን ለዓለም የምናስተዋውቅበት የሶፍት ፓወር መሣሪያችን ሲሆን የዲጂታል ኢኮኖሚው ደግሞ ከዘመኑ የቴክኖሎጂ ፍጥነት ጋር እኩል እንድንራመድ የሚያደርገን የህልውናችን ወሳኝ ቁልፍ ሆኗል።
የታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ የሉኣላዊነታችን መከበር ትልቁ ማሳያ ነው። ዓለም አቀፍ ጫናዎችን ተቋቁመን ግድቡን ከዳር ማድረሳችን፣ ወደ ብሪክስ (BRICS) አባልነት መቀላቀላችን እና የባህር በር ጥያቄያችንን በዲፕሎማሲያዊ መንገድ ለማሳካት የምናደርገው ትጋት ሀገራችን በዓለም አቀፍ መድረክ ያላትን ተሰሚነት እና ሉዓላዊ ክብሯን በተጨባጭ የሚያሳዩም ናቸው።
ይሁን እንጂ፣ እነዚህ ታላላቅ ሀገራዊ ስኬቶችና የዲፕሎማሲ ድሎች ዘላቂና ሙሉ ትርጉም የሚኖራቸው በውስጣችን ሰላምና ሀገራዊ መግባባት ሲሰፍን ብቻ መሆኑን መዘንጋት የለብንም። የልዩነት ግንቦችን አፍርሰን በጠረጴዛ ዙሪያ በሀገራዊ ምክክር ካልተወያየን እንዲሁም የጋራ ጠላታችን በሆነው ድህነት ላይ በአንድነት ካልዘመትን፣ የጀመርነውን የብልጽግና ጉዞ ማሳካትና ሉዓላዊነታችንን ከውስጥም ከውጭም ማስጠበቅ እጅግ ይከብዳል። የኢኮኖሚና የዲጂታል ልዕልናን ለማረጋገጥ መነሻው የውስጥ ሰላምና የአንድነት መንፈስ ነው።
በሌላ በኩል ደግሞ ይህን ሁለንተናዊ የልማት ጉዞ እውን ለማድረግ የሀገርን ሉዓላዊነት እና የሕዝባችንን ሰላም ለማስጠበቅ ሌሊትና ቀን የሚተጋው፣ በቆራጥነትና በጀግንነት የተገነባው መከላከያ ሠራዊታችን ሚና በጉልህ የሚጠቀስ ነዉ፡፡
ሠራዊቱ ለሀገሩና ለህዝቡ ሲል ዛሬም ይፋለማል፣ ይዋደቃል፣ የተከበረ ህይወቱንም ይሰጣል። ይህ ሠራዊት ሀገሩን ከውጭና ከውስጥ ፀረ-ሰላም ኃይሎች በመጠበቅ የሉዓላዊነታችን ጠንካራ ዘብ በመሆን ለልማታችን ምቹ ሁኔታን ይፈጥራል።
የሠራዊቱን የጀግንነት ፈለግ በመከተል ሕዝብ በአንድነት ሲቆም፣ አገርን ከጠላት መጠበቅና ወደ ብልጽግና ማሻገር ይቻላል። ስለዚህም የሀገርን ድንበርና ሰላም በንቃት መጠበቅ እንዲሁም ለጸጥታ አካላት ጠንካራ ድጋፍና አጋርነት ማሳየት የሁሉም ዜጋ ግዴታ ነው።
ስለሆነም አሁን ጊዜው ታሪካዊ ጀግንነታችንን ወደ አዲስ ምዕራፍ የምናሸጋግርበት ወቅት ነው። ሀገራዊ ሉዓላዊነታችንን ዘላቂ ለማድረግ፣ ሁለንተናዊ ብልጽግናችንን ለማረጋገጥ እንዲሁም ትግላችንን ከጦር ሜዳ ወደ ዲጂታል ፈጠራ፣ ከተረጂነት ወደ አምራችነት እና ወደ ጠንካራ የስራ ባህል የምናሸጋግርበት ወሳኝ የለውጥ ዘመን ላይ እንገኛለን። የትናንት አባቶቻችን በደማቸው ያቆዩልንን ነጻነት፣ ዛሬ በላባችን፣ በእውቀታችን እና በፈጠራ ክህሎታችን ልናደምቀው ግድ ይለናል!
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
*******************
( የዕለቱ መልዕክት)
ትናንት የሀገር ዳር ድንበር በጀግኖች ደምና አጥንት ይጠበቅ ነበር። ዛሬ ግን የዓለማችን የጂኦ-ፖለቲካ መልክ እና የኃይል አሰላለፍ መሰረታዊ ለውጥ ሲያስተናግድ፣ የሉዓላዊነት ትርጓሜም እጅግ ጥልቅ የሆነ አዲስ ገጽታን ተላብሷል።
በ21ኛው ክፍለ ዘመን የኢትዮጵያ ሉዓላዊነት እና የህልውና ዋስትና የሚረጋገጠው ጂኦግራፊያዊ ድንበርን በጦር መሣሪያ በመጠበቅ ብቻ ሳይሆን በስንዴ ማሳዎቻችን ስፋት፣ በፋብሪካዎቻችን የማምረት አቅም እንዲሁም በዲጂታል ቴክኖሎጂ ብቃታችን ጭምር ነው።
እውነተኛ ነፃነት ማለት የራስን ትርክት በራስ አቅም መጻፍ መቻል፣ የራስን ህዝብ በራስ አቅም መመገብ እና የሀገርን ጉዳይ ያለ አንዳች የውጭ ጫና መወሰን መቻል ማለት ነው።
ይህ ሉዓለዊነት ከእርዳታ ጥገኝነት እና ከተረጂነት አዘቅት ተላቆ በምግብ ራስን መቻልን፣ ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ አቅም ማምረትን እና በከንቱ የሚባክኑ የተፈጥሮ ጸጋዎቻችንን ወደ ሀገራዊ ሀብት መቀየርን ማዕከል ያደረገ ነው።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) "ደሃ አይከበርም፤ እየለመነ የሚኖር ሀገር አይከበርም" ሲሉ የተናገሩት መራር ሀቅ፣ የዘመናችንን የሉዓላዊነት ትግል ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ ነው። ክብራችን በዓለም አቀፍ መድረክ ላይ ደምቆ የሚታየው፣ ቃላችንም የሚሰማው ፖሊሲዎቻችንን ያለማንም ጣልቃ ገብነት ማስፈጸም የሚያስችል የኢኮኖሚ ጡንቻ ስንገነባ ብቻ መሆኑን ይህ አዲስ እሳቤ ያስገነዝበናል።
ይህ ሁለንተናዊ የኢኮኖሚ እና የቴክኖሎጂ ሉዓላዊነት እርስበርስ በተሳሰሩ ጠንካራ ምሰሶዎች ላይ የቆመ ነው። የግብርናው ዘርፍ ዜጎችን ከረሃብ ከመታደግ አልፎ፣ ሀገርን በእርዳታ ስም ከሚመጣ የፖለቲካ ተጽዕኖ እና የውጭ ጫና ነጻ የማውጣት አቅም አለው።
ከዚህ ጎን ለጎን አምራች ኢንዱስትሪውና ማዕድን ልማቱ የውጭ ምንዛሬን በማስገኘት ሀገራዊ ሜጋ ፕሮጀክቶቻችንን በራሳችን አቅም እንድንገነባና ኢኮኖሚያችን እንዲጠናከሩ እያደረጉ ይገኛሉ። የቱሪዝም ዘርፉ የብሔራዊ ገጽታችንን ከመገንባት ባሻገር ባህላችንን ለዓለም የምናስተዋውቅበት የሶፍት ፓወር መሣሪያችን ሲሆን የዲጂታል ኢኮኖሚው ደግሞ ከዘመኑ የቴክኖሎጂ ፍጥነት ጋር እኩል እንድንራመድ የሚያደርገን የህልውናችን ወሳኝ ቁልፍ ሆኗል።
የታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ የሉኣላዊነታችን መከበር ትልቁ ማሳያ ነው። ዓለም አቀፍ ጫናዎችን ተቋቁመን ግድቡን ከዳር ማድረሳችን፣ ወደ ብሪክስ (BRICS) አባልነት መቀላቀላችን እና የባህር በር ጥያቄያችንን በዲፕሎማሲያዊ መንገድ ለማሳካት የምናደርገው ትጋት ሀገራችን በዓለም አቀፍ መድረክ ያላትን ተሰሚነት እና ሉዓላዊ ክብሯን በተጨባጭ የሚያሳዩም ናቸው።
ይሁን እንጂ፣ እነዚህ ታላላቅ ሀገራዊ ስኬቶችና የዲፕሎማሲ ድሎች ዘላቂና ሙሉ ትርጉም የሚኖራቸው በውስጣችን ሰላምና ሀገራዊ መግባባት ሲሰፍን ብቻ መሆኑን መዘንጋት የለብንም። የልዩነት ግንቦችን አፍርሰን በጠረጴዛ ዙሪያ በሀገራዊ ምክክር ካልተወያየን እንዲሁም የጋራ ጠላታችን በሆነው ድህነት ላይ በአንድነት ካልዘመትን፣ የጀመርነውን የብልጽግና ጉዞ ማሳካትና ሉዓላዊነታችንን ከውስጥም ከውጭም ማስጠበቅ እጅግ ይከብዳል። የኢኮኖሚና የዲጂታል ልዕልናን ለማረጋገጥ መነሻው የውስጥ ሰላምና የአንድነት መንፈስ ነው።
በሌላ በኩል ደግሞ ይህን ሁለንተናዊ የልማት ጉዞ እውን ለማድረግ የሀገርን ሉዓላዊነት እና የሕዝባችንን ሰላም ለማስጠበቅ ሌሊትና ቀን የሚተጋው፣ በቆራጥነትና በጀግንነት የተገነባው መከላከያ ሠራዊታችን ሚና በጉልህ የሚጠቀስ ነዉ፡፡
ሠራዊቱ ለሀገሩና ለህዝቡ ሲል ዛሬም ይፋለማል፣ ይዋደቃል፣ የተከበረ ህይወቱንም ይሰጣል። ይህ ሠራዊት ሀገሩን ከውጭና ከውስጥ ፀረ-ሰላም ኃይሎች በመጠበቅ የሉዓላዊነታችን ጠንካራ ዘብ በመሆን ለልማታችን ምቹ ሁኔታን ይፈጥራል።
የሠራዊቱን የጀግንነት ፈለግ በመከተል ሕዝብ በአንድነት ሲቆም፣ አገርን ከጠላት መጠበቅና ወደ ብልጽግና ማሻገር ይቻላል። ስለዚህም የሀገርን ድንበርና ሰላም በንቃት መጠበቅ እንዲሁም ለጸጥታ አካላት ጠንካራ ድጋፍና አጋርነት ማሳየት የሁሉም ዜጋ ግዴታ ነው።
ስለሆነም አሁን ጊዜው ታሪካዊ ጀግንነታችንን ወደ አዲስ ምዕራፍ የምናሸጋግርበት ወቅት ነው። ሀገራዊ ሉዓላዊነታችንን ዘላቂ ለማድረግ፣ ሁለንተናዊ ብልጽግናችንን ለማረጋገጥ እንዲሁም ትግላችንን ከጦር ሜዳ ወደ ዲጂታል ፈጠራ፣ ከተረጂነት ወደ አምራችነት እና ወደ ጠንካራ የስራ ባህል የምናሸጋግርበት ወሳኝ የለውጥ ዘመን ላይ እንገኛለን። የትናንት አባቶቻችን በደማቸው ያቆዩልንን ነጻነት፣ ዛሬ በላባችን፣ በእውቀታችን እና በፈጠራ ክህሎታችን ልናደምቀው ግድ ይለናል!
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
3 days ago
(ዘ-ሐበሻ ሕይወት)) አደጋው ከተፈጸመ እነሆ አንድ ወር አልፎታል። የ50 ዓመቷን ኢትዮጵያዊት ሰርክአዲስ አበበ በቀለን ህይወት በከፍተኛ ስካር አሽከርክራ የቀጠፈችው የ28 ዓመቷ ማሪ ባህንድዋ፣ አሁን ላይ እስከ 20 ዓመታት ሊደርስ የሚችል የጽኑ እሥራት ፍርድ ከፊቷ ተደቅኗል። በጆርጂያ ግዛት ህግ መሰረት፣ አንደኛ ደረጃ የተሽከርካሪ ግድያ ብቻውን ከ3 እስከ 15 ዓመት የሚያስቀጣ ሲሆን፣ ከዚህ ጋር የተደራረቡት ሁለት የDUI (በስካር ማሽከርከር) እና የቸልተኝነት ወንጀሎች ሲታከሉበት፣ ማሪ የወጣትነት ዘመኗን ሙሉ በጨለማ የብረት አጥር ውስጥ እንድታሳልፍ ሊያደርጋት ይችላል።
ነገሩን ይበልጥ አሳዛኝ እና ልብ ሰባሪ የሚያደርገው ከግድያው ጀርባ ያለው የአደጋው መነሻ ምክንያት ነው። ማሪ የዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ብሔራዊ ቡድን የነፍስ ደጋፊ ነበረች። አደጋው ከመከሰቱ አንድ ቀን ቀደም ብሎ በአትላንታ ከተማ የተካሄደውን የኮንጎ የዓለም ዋንጫ ጨዋታ ስትከታተል እና በከፍተኛ ስሜት ስታከብር ውላለች። በዚያች ሌሊት በከፍተኛ ስካር ውስጥ ሆና ስታሽከረክረው የነበረው ጂፕ (Jeep Wrangler) መኪናዋ ላይም፣ የኮንጎ ደጋፊ መሆኗን የሚገልጹ ጽሁፎች እና መፈክሮች ተለጥፈውበት ነበር።
የኮንጎን እግር ኳስ ጨዋታ ድምቀት በከፍተኛ የአልኮል ስካር ታጅባ ስታከብር ያመሸችው ማሪ፣ የራሷን የደስታ ምሽት በንጹህ እግረኛ ደም አጥቅራዋለች። በዚያች የጭለማ ሌሊት ኮርትላንድ አቬኑ ላይ መንገዱን በሰላም እያቋረጠች የነበረችው ምስኪን ኢትዮጵያዊት፣ በመኪናዋ ላይ የኮንጎን መፈክር በለጠፈች እና ራሷን መቆጣጠር ባቃታት ሰካራም አሽከርካሪ የህይወት ጉዞዋ በድንገት እና በአሰቃቂ ሁኔታ ተቋጭቷል።
የአንዲት ሀላፊነት የጎደላት ግለሰብ የደስታ ስካር፣ የአንድን ኢትዮጵያዊት ቤተሰብ ለዘለዓለማዊ የሀዘን ማቅ አልብሷል። አሁን ፍርድ ቤቱ ማሪን ከህብረተሰቡ በማግለል ተመጣጣኝ የሆነውን የጽኑ እሥራት ቅጣት ያስተላልፋል ተብሎ በጉጉት የሚጠበቅ ሲሆን፣ ይህ አሳዛኝ ክስተት ግን በስካር የሚመጣ የሰከንድ ስህተት የሁለትን ሰዎች (የገዳይን እና የሟችን) ህይወት እንዴት ለዘለዓለም በጨለማ እንደሚያጠፋው ቁልጭ አድርጎ ያሳየ መሪር ትምህርት ሆኖ አልፏል።
ነገሩን ይበልጥ አሳዛኝ እና ልብ ሰባሪ የሚያደርገው ከግድያው ጀርባ ያለው የአደጋው መነሻ ምክንያት ነው። ማሪ የዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ብሔራዊ ቡድን የነፍስ ደጋፊ ነበረች። አደጋው ከመከሰቱ አንድ ቀን ቀደም ብሎ በአትላንታ ከተማ የተካሄደውን የኮንጎ የዓለም ዋንጫ ጨዋታ ስትከታተል እና በከፍተኛ ስሜት ስታከብር ውላለች። በዚያች ሌሊት በከፍተኛ ስካር ውስጥ ሆና ስታሽከረክረው የነበረው ጂፕ (Jeep Wrangler) መኪናዋ ላይም፣ የኮንጎ ደጋፊ መሆኗን የሚገልጹ ጽሁፎች እና መፈክሮች ተለጥፈውበት ነበር።
የኮንጎን እግር ኳስ ጨዋታ ድምቀት በከፍተኛ የአልኮል ስካር ታጅባ ስታከብር ያመሸችው ማሪ፣ የራሷን የደስታ ምሽት በንጹህ እግረኛ ደም አጥቅራዋለች። በዚያች የጭለማ ሌሊት ኮርትላንድ አቬኑ ላይ መንገዱን በሰላም እያቋረጠች የነበረችው ምስኪን ኢትዮጵያዊት፣ በመኪናዋ ላይ የኮንጎን መፈክር በለጠፈች እና ራሷን መቆጣጠር ባቃታት ሰካራም አሽከርካሪ የህይወት ጉዞዋ በድንገት እና በአሰቃቂ ሁኔታ ተቋጭቷል።
የአንዲት ሀላፊነት የጎደላት ግለሰብ የደስታ ስካር፣ የአንድን ኢትዮጵያዊት ቤተሰብ ለዘለዓለማዊ የሀዘን ማቅ አልብሷል። አሁን ፍርድ ቤቱ ማሪን ከህብረተሰቡ በማግለል ተመጣጣኝ የሆነውን የጽኑ እሥራት ቅጣት ያስተላልፋል ተብሎ በጉጉት የሚጠበቅ ሲሆን፣ ይህ አሳዛኝ ክስተት ግን በስካር የሚመጣ የሰከንድ ስህተት የሁለትን ሰዎች (የገዳይን እና የሟችን) ህይወት እንዴት ለዘለዓለም በጨለማ እንደሚያጠፋው ቁልጭ አድርጎ ያሳየ መሪር ትምህርት ሆኖ አልፏል።
3 days ago
ስቲቭ ሃርቪ: ለሦስት ዓመታት ያህል ቤት አልባ ነበር፤ መኪና ውስጥ ማደር ጀመረ
#ethiopia | ዛሬ በዓለም ዙሪያ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ሰዎች ስቲቭ ሃርቪን እንደ ስኬታማ የቴሌቪዥን አቅራቢ፣ ኮሜዲያን፣ ተዋናይ እና ደራሲ ያውቁታል።
እንደ "Family Feud" እና "Showtime at the Apollo" ያሉ ታዋቂ ፕሮግራሞችን በመምራት የሚታወቀው ሃርቪ፣ የሀብት እና የዝና ማማ ላይ ከመውጣቱ በፊት ግን እጅግ ፈታኝ የሆኑ የህይወት ምዕራፎችን አሳልፏል። የእሱ የህይወት ታሪክ ተስፋ የመቁረጥ፣ የእምነት እና የማያቋርጥ ጥረት ድንቅ ማሳያ ነው።
እንደ ዓለም አቀፍ የዜና አውታሮች ዘገባዎች፣ የስቲቭ ሃርቪ ጉዞ ሁልጊዜ አልጋ በአልጋ አልነበረም። በተለይም በ1980ዎቹ ውስጥ በኮሜዲው ዘርፍ ስራ ለመጀመር በሚጥርበት ወቅት፣ ለሦስት ዓመታት ያህል ቤት አልባ በመሆን በመኪናው ውስጥ ለመኖር ተገዷል። ይህ ጊዜ ለሃርቪ እጅግ ጨለማ እና ፈታኝ ነበር።
በኋላ ላይ ያንን ጊዜ ሲያስታውስ፣ "ስትመለከተው የሶስት ዓመት ጊዜ መሆኑን ማመን አልቻልኩም ነበር። ያኔ ትኩረቴ ሁሉ ከዛ ሁኔታ ለመውጣት ነበር። ወደፊት ለመራመድ በጣም ጠንክሬ እየሰራሁ ነበር" ብሏል። ይህ ንግግሩ ያሳለፈውን ጥልቅ ጭንቀት እና ከሁኔታው ለመውጣት የነበረውን ጽናት ያሳያል።
በተያያዘው ምስል ላይ እንደሚታየው፣ የስቲቭ ሃርቪ ጉዞ ወሳኝ ምዕራፍ ያገኘው በአንድ ሆቴል የህዝብ መታጠቢያ ቤት ውስጥ ነው። በአንድ ወቅት እራሱን እያጠበ እያለ፣ የህይወቱ ዝቅተኛው ደረጃ ላይ እንደደረሰ ተሰማው። በዛ የጭንቀት ወቅት፣ ለፈጣሪው ቃል ኪዳን ገባ። "ካሳካህልኝ፣ እዛ ደረጃ ላይ ስደርስ ይህን ያደረግከው አንተ እንደሆንክ ለሁሉም እናገራለሁ" አለ።
ይህ ቃል ኪዳን ሃርቪን በፈተናዎች ውስጥ እንዲጸና እና ተስፋ እንዳይቆርጥ ያደረገው መንፈሳዊ ጥንካሬ ሆነ። ምስሉ ላይ “I was homeless and living in my car. I told God, 'If You let me make it, I'm going to tell everybody it was You.' So, I'm telling you about Him.” የሚለው ጥቅስ ይህንን ቃል ኪዳን እና ዛሬም ድረስ እያከበረው መሆኑን ያሳያል።
ለፈጣሪው ቃል ከገባ ከጥቂት ጊዜ በኋላ፣ ሃርቪ የቆመ ኮሜዲ ስራ እድል የሚሰጥ የስልክ ጥሪ ደረሰው። ይህ እድል ለሌሎች ስራዎች መንገድ ከፈተለት፣ በመጨረሻም በኒውዮርክ የሚገኘው "Showtime at the Apollo" የተሰኘው ታዋቂ ፕሮግራም አቅራቢ ሆነ።
ይህ ትልቅ እመርታ "The Steve Harvey Show," "Family Feud," እና ሌሎች በርካታ ፕሮግራሞችን ያካተተ የተሳካ የስራ ህይወት እንዲጀምር አደረገው።
ዛሬ ሃርቪ በቢሊዮን የሚቆጠሩ ተመልካቾች ያሉት ታዋቂ ሰው ቢሆንም፣ በዛ መታጠቢያ ቤት የገባውን ቃል ኪዳን ፈጽሞ አልረሳውም። ምንም እንኳን ስለ እምነቱ በግልፅ መናገሩ ትችት ቢያስከትልበትም፣ ሃርቪ ግን እምነቱን መግለጹን ቀጥሏል።
ከቤት አልባነት ወደ ስኬት ያደረገውን ጉዞ በማመልከት፣ "ህይወቴን ተመልከቱ። ከየት እንደመጣሁ ተመልከቱ። አሁን የት እንዳለሁ ተመልከቱ። እኔ የምጠቀመው (እምነት) እየሰራ ነው" ይላል።
የስቲቭ ሃርቪ የህይወት ታሪክ ከባድ ፈተናዎች እና ውድቀቶች መቋጫ ሳይሆኑ፣ ለትልቅ ስኬት መነሻ ሊሆኑ እንደሚችሉ ያስተምረናል።
በምስሉ ላይ እንደሚታየው፣ ሃርቪ በመኪና ውስጥ ከነበረበት ጭንቀት ወደ ስኬታማ ህይወት የተሸጋገረው በእምነት፣ በጠንካራ ስራ እና ተስፋ ባለመቁረጥ ነው። የእሱ ጉዞ ለብዙዎች ተስፋ የመስጠት እና የማበረታታት አቅም ያለው፣ እውነተኛ የጽናት ታሪክ ነው።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#ethiopia | ዛሬ በዓለም ዙሪያ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ሰዎች ስቲቭ ሃርቪን እንደ ስኬታማ የቴሌቪዥን አቅራቢ፣ ኮሜዲያን፣ ተዋናይ እና ደራሲ ያውቁታል።
እንደ "Family Feud" እና "Showtime at the Apollo" ያሉ ታዋቂ ፕሮግራሞችን በመምራት የሚታወቀው ሃርቪ፣ የሀብት እና የዝና ማማ ላይ ከመውጣቱ በፊት ግን እጅግ ፈታኝ የሆኑ የህይወት ምዕራፎችን አሳልፏል። የእሱ የህይወት ታሪክ ተስፋ የመቁረጥ፣ የእምነት እና የማያቋርጥ ጥረት ድንቅ ማሳያ ነው።
እንደ ዓለም አቀፍ የዜና አውታሮች ዘገባዎች፣ የስቲቭ ሃርቪ ጉዞ ሁልጊዜ አልጋ በአልጋ አልነበረም። በተለይም በ1980ዎቹ ውስጥ በኮሜዲው ዘርፍ ስራ ለመጀመር በሚጥርበት ወቅት፣ ለሦስት ዓመታት ያህል ቤት አልባ በመሆን በመኪናው ውስጥ ለመኖር ተገዷል። ይህ ጊዜ ለሃርቪ እጅግ ጨለማ እና ፈታኝ ነበር።
በኋላ ላይ ያንን ጊዜ ሲያስታውስ፣ "ስትመለከተው የሶስት ዓመት ጊዜ መሆኑን ማመን አልቻልኩም ነበር። ያኔ ትኩረቴ ሁሉ ከዛ ሁኔታ ለመውጣት ነበር። ወደፊት ለመራመድ በጣም ጠንክሬ እየሰራሁ ነበር" ብሏል። ይህ ንግግሩ ያሳለፈውን ጥልቅ ጭንቀት እና ከሁኔታው ለመውጣት የነበረውን ጽናት ያሳያል።
በተያያዘው ምስል ላይ እንደሚታየው፣ የስቲቭ ሃርቪ ጉዞ ወሳኝ ምዕራፍ ያገኘው በአንድ ሆቴል የህዝብ መታጠቢያ ቤት ውስጥ ነው። በአንድ ወቅት እራሱን እያጠበ እያለ፣ የህይወቱ ዝቅተኛው ደረጃ ላይ እንደደረሰ ተሰማው። በዛ የጭንቀት ወቅት፣ ለፈጣሪው ቃል ኪዳን ገባ። "ካሳካህልኝ፣ እዛ ደረጃ ላይ ስደርስ ይህን ያደረግከው አንተ እንደሆንክ ለሁሉም እናገራለሁ" አለ።
ይህ ቃል ኪዳን ሃርቪን በፈተናዎች ውስጥ እንዲጸና እና ተስፋ እንዳይቆርጥ ያደረገው መንፈሳዊ ጥንካሬ ሆነ። ምስሉ ላይ “I was homeless and living in my car. I told God, 'If You let me make it, I'm going to tell everybody it was You.' So, I'm telling you about Him.” የሚለው ጥቅስ ይህንን ቃል ኪዳን እና ዛሬም ድረስ እያከበረው መሆኑን ያሳያል።
ለፈጣሪው ቃል ከገባ ከጥቂት ጊዜ በኋላ፣ ሃርቪ የቆመ ኮሜዲ ስራ እድል የሚሰጥ የስልክ ጥሪ ደረሰው። ይህ እድል ለሌሎች ስራዎች መንገድ ከፈተለት፣ በመጨረሻም በኒውዮርክ የሚገኘው "Showtime at the Apollo" የተሰኘው ታዋቂ ፕሮግራም አቅራቢ ሆነ።
ይህ ትልቅ እመርታ "The Steve Harvey Show," "Family Feud," እና ሌሎች በርካታ ፕሮግራሞችን ያካተተ የተሳካ የስራ ህይወት እንዲጀምር አደረገው።
ዛሬ ሃርቪ በቢሊዮን የሚቆጠሩ ተመልካቾች ያሉት ታዋቂ ሰው ቢሆንም፣ በዛ መታጠቢያ ቤት የገባውን ቃል ኪዳን ፈጽሞ አልረሳውም። ምንም እንኳን ስለ እምነቱ በግልፅ መናገሩ ትችት ቢያስከትልበትም፣ ሃርቪ ግን እምነቱን መግለጹን ቀጥሏል።
ከቤት አልባነት ወደ ስኬት ያደረገውን ጉዞ በማመልከት፣ "ህይወቴን ተመልከቱ። ከየት እንደመጣሁ ተመልከቱ። አሁን የት እንዳለሁ ተመልከቱ። እኔ የምጠቀመው (እምነት) እየሰራ ነው" ይላል።
የስቲቭ ሃርቪ የህይወት ታሪክ ከባድ ፈተናዎች እና ውድቀቶች መቋጫ ሳይሆኑ፣ ለትልቅ ስኬት መነሻ ሊሆኑ እንደሚችሉ ያስተምረናል።
በምስሉ ላይ እንደሚታየው፣ ሃርቪ በመኪና ውስጥ ከነበረበት ጭንቀት ወደ ስኬታማ ህይወት የተሸጋገረው በእምነት፣ በጠንካራ ስራ እና ተስፋ ባለመቁረጥ ነው። የእሱ ጉዞ ለብዙዎች ተስፋ የመስጠት እና የማበረታታት አቅም ያለው፣ እውነተኛ የጽናት ታሪክ ነው።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
Sponsored by
Surafel
3 days ago
“ታሪክ በትዝታ ላይ የተጫነ ሸክም አይደለም-የነፍስ መገለጥ እንጂ”
ጋዜጠኛ ዮናስ አየለ እንደጻፈው
ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ ከአሚኮ ጋር ያደረጉትን ቃለምልልስ አዳምጬ እንደጨረስኩ በቃለ ምልልሱ በርዕሰ ጉዳይ ደረጃ ጎልተው ከወጡ ዋና ዋና ጭብጦች መካከል አንዱ ነገረ ታሪክ እንደሆነ ተሰምቶኛል፡፡ ታሪክ-የሀገር ውስጥና የውጭ፤ የሩቅና የቅርብ ዘመን! ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቃለ ምልልሳቸው ያንጸባረቁትን ሚዛናዊና አምክኖአዊ የታሪክ እይታና ድምዳሜያቸውን አለማድነቅ ንፉግነት ነው፡፡ የአሥራ ዘጠነኛው ክፍለ ዘመን እንግሊዛዊ የታሪክ ጸሐፊና ፖለቲከኛ ሎርድ አክተን “History is not a burden on the memory but an illumination of the soul” ብሎ ሲጽፍ “ታሪክ የነፍስ መገለጥ እንጂ በትዝታ ላይ የተጫነ ሸክም አይደለም” ማለቱ ነበር፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቃለ ምልልሳቸው ያነሷቸው የታሪክ አንኳር ጉዳዮች እስከዛሬ ድረስ በሀገራችን የታሪክ አጻጻፍ(Historiography) እና በሕዝባዊ ትርክቶቻችን(በሚዲያዎችን ጭምር) በሚገባቸው ልክ ያልተወሱ፤ ቢወሱም ፈራ ተባ እየተባሉ የሚጠቀሱ፤ አለፍሲልም ባልተገባ የፖለቲካ እይታ ደንቃራ ተደርገው የተወሰዱ የታሪክ ግርዶሽ(eclipse of the history) ሆነው የኖሩ ስብራቶቻችን ነበሩ፡፡ ከነዚህ ቁልፍ ጉዳዮች መካከል ዋነኛዎቹ አንዱ የሕዝቦች ትስስር እና መስተጋብር ታሪክ ሲሆን ሌላኛው በአገረ መንግስት ምሥረታ ውስጥ የሸዋ ጂኦ-ስትራቴጂካዊ ሚናን የተመለከቱት ናቸው፡፡
በመጀመሪያ የአማራና የኦሮሞ ሕዝቦች በኩታ ገጠም ቀዬዎቻቸው እና የታሪክ እድል በፈጠረላቸው የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚና የባህል አጋጣሚዎች እንደሌሎች ማህበረሰቦች ሁሉ መጋባት መዋለዳቸው፤መተሳሰር መዋሀዳቸው ሀቅ የመሆኑን ያህል የታሪክ ጥናት እና የትርክቶቻችን ማጠንጠኛ አለመሆናቸው ይታወቃል፡፡ ከዚህ በባሰ ሁኔታ ደግሞ በነገሥታቱ መካከል የነበረው የፖለቲካ ጋብቻና የመሪዎቻችን ማህበራዊ መሠረት ጉዳይ ነውር እስኪመስል በእውነታው ልክ ሳይጠናና፣ሳይነገርለት ዘመናት አልፈዋል ፡፡ በሌላ በኩል በሸዋና አካባቢው ለረዥም ዘመን የኖሩ ሕዝቦች በአገረ መንግሥት ግንባታ ሂደት የተጫወቱት ሚናና የሚጋሩት ቀደምት የሥልጣኔ ባለቤትነት (ታሪክ ሰሪነት-Agency) ግጥምጥሞሽ በሀገር መሪ ደረጃ መወሳታቸው እጅግ ጉልህ ፋይዳ ያለው ጉዳይ ነው ፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቃለ ምልልሳቸው ያነሷቸው የታሪክ እውነታዎች ያለጥርጥር ታሪካችንንና የታሪክ ምልከታችንን ደጋግመን መመርምር እንዳለብን የሚያስገነዝቡና የወገንተኝነት ጥያቄ በሚነሳባቸው ሃይማኖታዊ የታሪክ ምንጮች እንኳን የተቀመጡ ገሃድ እውነታዎች ናቸው፡፡ መመርመር ለሚፈልግ አጥኚ እነዚህ የታሪክ እውነታዎች በየነገሥታቱ ዜና መዋዕሎች (የዐጼ አምደ ጽዮን፣ ዐጼ ሱስንዮስ፣የዐጼ ገላውዲዮስ፣ የዐጼ ሠርጸ ድንግል ወዘተ)፤ የሃይማኖት ሰነዶች፣ የታሪከ ነገሥት ቅጂዎች፣ ወደ ኢትዮጵያ መጥተው የነበሩ አውሮፓውያን ተጓዦችና ጸሐፊያን (ፍራንስስኮ አልቫሬዝ፣ ፔድሮ ፔዝ፣ ማኑኤል አልሜዳ፣ ጄሮኒሞ ሎቦ፣ ጀምስ ብሩስ፣ ኮንቲ ሮሲኒ ወዘተ ) መዝግበው በተውልን ሰነዶች ሰፍረው የምናገኛቸው፤ ከትውልድ ወደ ትውልድ ሲተላለፉ የኖሩ ቱባ መረጃዎች ናቸው፡፡
ፍራንሲስኮ አልቫሬዝ የተወልን የጽሑፍ ሰነድና ሌሎች ሀገርኛ የቃል መረጃ ምንጮች ዐፄ ልብነድንግል(1498-1532 ዓ.ም.) እንደ መሪ የአማራና የኦሮሞ ብቻ ሳይሆን ምናልባትም የሌሎች ሕዝቦችም ማህበራዊ ዳራ የነበራቸው ንጉሠ ነገሥት እንደሆኑ የሚያስረዱ ሲሆን አልቫሬዝ የንጉሱ የእናት ወንድም የነበሩት አጎታቸው ዶሪ ባህረ ነጋሽ ኦሮሞ እንደነበሩና ባህረ ነጋሽ ዶሪ ሲሞቱ ሥልጣኑ በቀጥታ ወደልጃቸው ቡሎ መሸጋገሩን ጭምር በአይኑ ያየውን ጽፏል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ በትኩረት መታየት የሚገባው ጉዳይ ስለዐጼ ልብነ ድንግል የጦር አዛዦች የተነገሩ የቃል መረጃዎች ናቸወ፡፡ ከእነዚህ መካከል የንጉሠ ነገሥቱ ሠራዊት የቦረንትቻ ባሕል ያውቅ እንደነበር በተክለጻዲቅ መኩሪያ መጻፉና ከዐጼ ልብነድንግል የጦር አዛዦች አንዱ የነበረው ቱሉ ደገልሀን በመራው ከኢማም አሕመድ ጋር የተካሄደ ጦርነት የዐጼው ጦር ሲያፈገፍግ ንጉሠ ነገሥቱ “ሁሉም ቢፈራ ቱሉ እንዴት ፈራ? ” ማለታቸው ስለሠራዊታቸው ሥብጥር የሚነግረን ነገር አለ፡፡
ኦቶማን ቱርኮችን እና የዘመኑ ተላላኪዎቻቸውን ለመዋጋት የንጉሠ ነገሥቱ ሠራዊት አንድ አካል ሆነው እስከ ኤርትራ ድረስ ዘምተው ስለነበሩ የኦሮሞ ተዋጊዎች ተጋድሎ የዐጼ ሠርጸድንግል(1542-1590 ዓ.ም.) ዜና መዋእል በግልጽ አስፍሯል፡፡ እነዚህ የኦሮሞና የሌሎች ሕዝቦች ተወላጅ ወታደሮች ትግራይ እንጢጮ አካባቢ ያካሄዱትን አውደ ውጊያ ዜና መዋዕሉ ይተርካል፡፡ ለመንግሥታቸውና ለሀገራቸው እስከባሕር ጠረፍ ድረስ ዘምተው ዋጋ መክፈላቸውም ተመዝግቧል፡፡ የዐጼ ሱስንዮስ(1607-1632 ዓ.ም.) ዜና መዋእል እና በዘመኑ ኢትዮጵያ መጥተው የነበሩ የአውሮፓ(የፖርቱጋል) ተጓዦች የጻፏቸው የመረጃ ምንጮች ንጉሠ ነገሥቱ ግንደበረት፣ሐምቦና አካባቢው ቤታቸው እንደነበር፤ አጎታቸው ለማሞ እንደሚባል፣ ወላጅ እናታቸው(ሐመልማል ወርቅ) የአዛዥ ኩሎ ልጅ የነበረች፤ የዚሁ የሐመልማል ወርቅ ጎሳ ተወላጅ የሆነ ቡኮ የተባለ ኦሮሞና ሠራዊቱ ለአባይ ቅርብ የሆነች ምዕራብ ሸዋ ላይ ዐጼ ሱስንዮስ ሲያገኙት የነበረውን ደስታና የፍቅሩን ጽናት ዜና መዋዕሉ ሳይሰስት ጽፎታል፡፡ ዐጼ ፋሲል(ከ1632 እስከ 1667 ዓ.ም.) አባቱ ሱስንዮስ እናቱ የወሎ ቃሉ ሰው(እቴጌ ሥልጣን ሞገሳ የሚል ስም የተሰጣት) እንደሆነች የታሪክ ምንጮች ያስረዱናል፡፡ በ1620ዎቹ ዓመታት ጀምሮ በኢትዮጵያ ይኖር የነበረው ፖርቱጋላዊ ቄስ ጄሮኒሞ ሎቦ ስለዐጼ ፋሲል እናትና ኦሮሞ ዘመዶቻቸው በአይን ምስክርነት የሚያውቀውን ጽፏል፡፡ የእቴጌ ሥልጣን ሞገሳ አያት ስለብዝሀ ሃይማኖት አስፈላጊነት የነበራቸውን ግልጽ ፖሊሲ ጭምር ሎቦ ዘግቦታል፡፡ የዐጼ በካፋ(1721-1730 ዓ.ም.) እና የዐጼ ኢዮአስ(1747-1761 ዓ.ም.) ጎንደር መቼም ለሕዝቦች ውህደትና ትስስር ጥሩ ማሳያ ነበረች፡፡ የየጁ ኦሮሞ ገዢ የነበረው የአሚቶ ሴት ልጅ ዝነኛዋ ውቢት ልጇ ዐጼ አዮአስ ነበር፡፡ ኢዮአስ ከኦሮሞ አጎቱ ከደጃች ሉቦ ጋር ሥልጣኑን በጎንደር እንዴት እንዳጸና፤ የቤተ መንግሥቱም የሥራ ቋንቋ አፋን ኦሮሞ እንደነበረ የንጉሠ ነገሥቱ ዜና መዋዕልና በጀምስ ብሩስ ቅጽ ሁለት መጽሀፍ የተመዘገቡ የታሪክ መረጃዎች ያስረዱናል፡፡
መነሻውን ወሎ በማድረግ ጎንደር ጸንቶ የኖረው የየጁ ሥርወ መንግሥት(ወረ ሼኮች) መሥራቾች የመርሳው አባ ጌትዬ፣ የልጃቸው ጓንጉል አባ ሴሩ እንዲሁም የልጅ ልጃቸው የራስ አሊ ጓንጉል(አሊ ትልቁ) ታሪክ በኢዮአስ ዜና መዋዕል፣ በጀምስ ብሩስ መጽሐፍና በሌሎች በርካታ ሰነዶች ታሪካቸው ተዘግቧል፡፡ በኋላ ላይ በሽፈራው በቀለ(ፕሮፌሰር) እና ሞላ ትኩዬ የቀረቡ ጥልቅ ጥናቶች ይህን እውነት በዝርዝር ያስረዱናል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቃለ ምልልሳቸው እንደጠቀሱት የእነዚህ መሪዎች የፖለቲካ ጋብቻ ታሪክ የሚያሳየን በሄዱበት አገር ሁሉ የሕዝቦች ትሥሥር እና የፖለቲካ ጋብቻ የኖረ ታሪካችን እና የጉልበታችን ምንጭ እንደነበረ ነው፡፡ በዳግማዊ ዐጼ ቴዎድሮስ ዘመን የተጻፉ የታሪክ ሰነዶች የወሎዋ ገዢ ወርቂቱ ወዳጆ(የማመዶች ሥርወ መንግሥት መሪ የኢማም አሊ አባ ቡላ ባለቤት) ንጉሥ ምኒልክ ከመቅደላ እስር ቤት እንዲያመልጡ ያደረጉ፤ አጃቢ ሠራዊት አሰማርተው ምኒልክን እስከሸዋ የሸኙ እንደነበሩ በዋናነት ከጸሓፌ ትእዛዝ ገብረ ሥላሴ ታሪከ ዘመን ዘ ዳግማዊ ምኒልክ ዜና መዋዕል እና በመቅደላ አምባ እስር ላይ የነበሩ አውሮፓውያን ከጻፏቸው መረጃዎች እንረዳለን፡፡
ሥልጣኔዎቻችን ሁሉ ተደምረን ያሳካናቸው እንደሆነ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቃለ ምልልሳቸው አንስተዋል፡፡ የዐድዋ ዘመቻና ድሉ ለዚህ አንዱ ማሳያ እንደሆነ ተጨባጭ የታሪክ ምንጮች ያስረዱናል፡፡ በ1888 ዓ.ም. ለዓድዋ ዘመቻ ከመላው ኢትዮጵያ የተመመው ሠረዊት ወፍላ ላይ የነበረው ሠልፍ የንጉሠ ነገሥቱ ዜና መዋዕል እንኳን እንዲህ ይገልጸዋል፡፡ “የመኳንንቱ የጦር መሣሪያ፣ወርቁ፣ ጣፋ፣ ብሩ፣ ሙጣው፣ ጫሜው፣ ሎሚታውና ኩፊታው፣ ከሌቻው፣ ወርቅ ለምዱ እንደጸሐይ ሲያበራ ዋለ፡፡” እንደጸሐይ የበራውን ሕብረ ባሕልና ሕብረ ማንነት ትርክቶቻችን በልኩ አጉልተው ያውቃሉ?
ሸዋና አካባቢው(ወሎን ጨምሮ) እንደ አንድ ጂዞ ስትራቴጂ ሥፍራ የሕዝቦች ውህደትና ትስስር መሠረት ሆኖት የመልክዓ ምድር መገኛው ለግብርና እና ለውጭ ንግድ የተመቸ በመሆኑ በኢትዮጵያ አገረ መንግሥት ግንባታ ታሪክ ውስጥ ቁልፍ ቦታ ይዞ መኖሩን ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቃለ ምልልሳቸው መግቢያ አስታውሰውናል፡፡ ሸዋና አካባቢው ከመንግሥታት ምስረታ ጋር በተገናኘ ከዘጠነኛው አንስቶ እስካሁን ያለው ረዥም የታሪክ ጉዞ በርግጥም ሊነገር፣ ሊተነተን የአደባባይ ትርክት አካል ሊደረግ የሚገባው እውነት ነው፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከሸዋ ሡልጣኔት ምስረታ( እ.አ..አ.896 ዓ.ም.) እስከ ዓድዋ ድል(1888 ዓ.ም.) ሥላወሷቸው የአርጎባ(የወላስማ/ወሊ አስማ ሥርወ መንግሥት)፣ የአማራ(ሰለሞናዊ ሥርወ መንግሥት)፣ ኦሮሞ(ቱለማው በተለይ)፣ወርጂ፣ ጉራጌ፣ ጋፋት፣ ወዘተ ሕዝቦች ትስስርም ይሁን የፖለቲካ ጋብቻ የተመለከተ ታሪክ ከበቂ በላይ የታሪክ ማስረጃ ምንጮች ቢኖሩንም በታሪክ ግርዶሹ ምክንያት የወል ትርክት አካል መሆን አልቻለም፡፡
ኤንሪኮ ቼሩሊ ከሐረር አግኝቶ ያሳተመው በአረብኛ የተጻፈው የሸዋ ሡልጣኔት ዜና መዋዕል እንደሚያመለክተው ሡልጣኔቱን እ.አ.አ. በ896/7 የመሰረቱት የማህዙሚ ጎሳ አባላት ናቸው፡፡ መንግሥታቸውም ከ9ኛው እስከ 13ኛው ክፍለ ዘመን ድረስ በተከታታይ በገዙ አሥራ አራት ሱልጣኖች እንደጸና የታሪክ መረጃ ምንጮች ያመለክታሉ፡፡ የሸዋ ሙስሊም ሡልጣኔቱ መቀመጫ ከተማ ከአዲስ አበባ በስተሰሜን ምሥራቅ 70 ኪሎ ሜትር ላይ የምትገኝ ወለላ የተባለች ሥፍራ እንደነበረች የጆርጅ ደብሊው ቢ ሀንቲንግፎርድ(1989) ጥናት ያመለክታል፡፡ የማህዙሚ ሥርወ መንግሥት ከመጨረሻዎቹ መሪዎች አንዱ የነበረው ሡልጣን ድልመራህ ወርጂዎች የይኖሩበት በነበረው አካባቢ በ1270ዎቹ በነበረ የርስ በርስ ጦርነት ድል ሳይቀናው ሲቀር ሕይወቱን ለማትረፍ ዐጼ(የአማራ ገዥ?) እንደሄደ ይህው የአረብኛ ዜና መዋእል ያስረዳል፡፡ የማህዙሚዎች የሸዋ ሡልጣኔት የተተካው በዋናነት የአርጎባዎች አገር በሆነው ይፋት(ዊፋት) ላይ በወላስማዎች ነበር፡፡ ወላስማዎች ከአጎራባቾቻው ጋር እየተጋቡ፣ እየተስማሙም እየተጋጩም የይፋት ሡልጣኔትን ከ13ኛው እስከ 15ኛው ክፍለ ዘመን ከሸዋ እስከ ምሥራቃዊ የኢትዮጵያ ጠረፍ እንዳስተዳደሩ ስፍር ቁጥር የሌለው የሰነድ( የኢብን ካልዱን ተማሪ የነበረው አል ማቅሪዚ ጽሑፍ- ኪታብ አል ኢልማም)፣ የአርኪዮሎጂና የቃል መረጃ ምንጮች አሉ፡፡
መነሻውን ሰሜን ሸዋ እና ደቡብ ወሎ ያደረገው የክርስቲያኑ ሰሎሞናዊ ሥርወ መንግሥት በአካባቢው ያሉ ሕዝቦች ተዋህደው ከ13ኛው ክፍለ ዘመን ጀምሮ በጋራ የመሠረቱት እንደሆነ አያጠያይቅም፡፡ አማራዎች፤ አርጎባዎች፣ ወርጂዎች፣ ጋፋቶች፣ ጉራጌዎች እና ኦሮሞዎች፣ አፋሮች፣ ሐረሪዎች ወዘተ በዚህ የሸዋ መንግሥታት የተጽዕኖ ምህዳር(Orbit) ውስጥ እንደሚገኙ ዜና መዋእሎች፣ የሃይማኖት ሰነዶች፣ የአርኪዮሎጂ ማስረጃዎች ከትውልድ ወደ ትውልድ ሲተላለፉ የኖሩ የቃል መረጃ ምንጮች ያመለክታሉ፡፡ ለምሳሌ ታደሠ ታምራት(ፕሮፌሠር) ከ13ኛው እስከ 16ኛው ክፍለ ዘመን የቤተ ክርስቲያንና መንግሥትን ግንኙነት ታሪክ ባጠኑበት መጽሐፋቸው የገላንና ያያ ሰዎች ሸዋ ውስጥ በ13ኛው ክፍለ ዘመን በኦዳ ዛፍ (ኮቢል የሚባል ዋርካ) ሥር ሃይማኖታዊ ሥርዓት ይፈጽሙ እንደነበር ገድለ አቡነ ቀውስጦስን ጠቅሰው ጽፈዋል(ገጽ 184)፡፡ ሸዋ የባለ ብዙ ማንነት ሕዝቦች ሀገር ከመሆኗ ባሻገር በ16ኛው ክፍለ ዘመን የተከናወኑ ዐበይት ጉዳዮች ላይ መረጃ የተወልን መነኩሴው አባ ባህሪይ እንደገለጸው “ሸዋ የመንግሥት ሀገር ነች” (ገጽ 130)፡፡ በየዘመናቱ ከሸዋ የተነሱ የፖለቲካ ኃይሎች፣ ፈረሰኛ ሠራዊታቸውን ይዘው በሰሜን እስከ ኤርትራ(በዐጼ ሠርጸ ድንግል ዘመን- የኤርትራዋ ባሬንቱ የዚህ የታሪክ ሂደት ውርስ አይደለችም ማለት አይቻልም፡፡) በምሥራቅ እስከ ዘይላ(ከዐጼ አምደጽዮን እስከ ገላውዲዮስ ዘመን)፣ በምዕራብ እስከ ሱዳን ፋዞግሊ(ዐጼ ሱስንዮስ ዘመን) በደቡብ እስከ ሞያሌ ተንቀሳቅሰው በአገረ መንግሥት ግንባታ ሂደት ውስጥ ቁልፍ ሚና ተጫተዋል፡፡
እነዚህ የሸዋ እና አካባቢው ሕዝቦችና ገዢዎች ትልቁን ንቅናቄያቸውን ያደረጉት ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን እንደሆነ ይታወቃል፡፡ ዐጼ ምኒልክና ራስ ጎበና ዳጬ የቱለማ ኦሮሞ፤ የሸዋ አማራ እና የሌሎችም ውህድ የሆነ ጦራቸውን አዝምተው ወሎ ወግተው ወረኢሉን የመንሥታቸው መቀመጫ ያደረጉት አርሲ፣ወለጋ፣ከሐረር ከመዝመታቸው በፊት ነበር፡፡ የመጫ ኦሮሞ ተወላጁን የጎጃሙን ንጉስ ተክለሃይማኖት(አዳል ተሰማ) በቱለማው መሪ ራስ ጎበና ዳጪ እምባቦ ላይ ያስገበሩት የጂኦ ፖለቲካዊ እና የሕዝቦች ትስስር እድሎች ጉልበት ፈጥሮላቸው፤ ኃይል አጎናጽፏቸው እንጂ በአጋጣሚ አይደለም፡፡ በርግጥ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የፖለቲካችን ደንቃራነት የፈጠረውን የታሪክ ግርዶሽ ያሸነፉ ፋና ወጊ ጥናቾች መውጣት ጀምረዋል፡፡ አንዱ “Invisible Actors: The Oromo and the Creation of Modern Ethiopia(1855-1913)” በሚል ርዕስ በብሪያን ጀምስ ዬትስ(2002) በኤሊኖይስ ዩኒቨርሲቲ ከተጠናው እጅግ ጠቃሚ የዶክትሬት ዲግሪ ማሟያ ጥናት ሲሆን ሌላው የደቻሳ አበበ(ዶ/ር) ጎበና ወታደራዊና ፖለቲካዊ ሕይወት ነው፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቃለ ምልልሳቸው የዘመናዊት ኢትዮጵያን እውን መሆን ያለ ምኒልክና ያለ ጎበና እንደማይታሰብ ሲጠቅሱ ይህንን እውነታ ማጉላታቸው ይመስለኛል፡፡
የሕዝቦች ትስስርና የፖለቲካ ጋብቻ በአማራና በኦሮሞ ሕዝብ መስተጋብር ብቻ የታጠረ አልነበረም-ሊሆንም አይችልም፡፡ የኢትዮጵያ ሕዝብ ባህልና ሥልጣኔ መጋመዱ ረቂቅ ነው፡፡ ከጥንታዊ አክሱም ዘመን ጀምሮ በዝነኞቹ የአክሱም መቃብር ሀውልቶች እና በላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናት ላይ ከምናገኛቸው የኪነ ሕንጻ ትእምርቶች(Symbols) መካከል የውሸት በሮች (False Doors) እና የውሸት መስኮቶች(False windows) የሙታን መንፈስ(ኤከራ) መመላለሻ እንደሆኑ በጥናት የተረጋገጠ ነው (ቢትራይስ ፕሌይን Annales d'Éthiopie 1965) ፡፡ ይህ የኤከራዎች መመላለስና የመነጋገር ባህል እና እምነት ከደቡባዊ ግብጽ አንስቶ እስከ ሰሜን ኬንያ ድረስ በሚኖሩ የኩሽ ሕዝቦች በሰፊው የሚታወቅ ረዥም ዘመን ያስቆጠረ ልምምድ ነው፡፡
ሌላው በልኩ ያልተጠና እና በትርክቶቻችን ውስጥ ትኩረት ያልተሰጠው በሕዝቦች መካከል ያለ ሥልጣኔ ትስስር ታሪክ የእያንዳዱን የዛግዌ ነገሥታት የሥልጣን ዘመናትን የተመለከተ ነው፡፡ ከታሪክ ነገሥት፣ ከልዩ ልዩ ዜና መዋዕሎች፣ ከፖርቱጋል ተጓዦች(ፓኤዝና አልሜዳ) ከብሪቲሽ ሙዝየም እንዲሁም ከኮንቲ ሮሲኒ የተገኙት ምንጮች የሚረጋግጡት የሁሉም የዛግዌ ዐጼዎች( ከአንድ ሁለቱ በስተቀር) የሥልጣን ዘመን 40፤40 ዓመታት ነበር፡፡ ይህ ጉዳይ በኦሮሞ የገዳ ሥርዓት የአንድ ትውልድ የሥልጣን ዑደት ጋር አንድ አይነት የሆነው በአጋጣሚ ነው ወይስ ዛግዌዎች እና ኦሮሞዎች የኩሽ ሕዝቦች በመሆናቸው ቀዳሚ ከሆነው የጋራ ሥልጣኔያቸው የሚቀዳ የአስተዳደር ሥርዓት ነው? እነዚህስ ሀቆች የወል ትርክቶቻችን መመሆን አለመቻላቸው በፖለቲካ ደንቃራነት የተፈጠረ የታሪክ ግርዶሽ(eclipse of history) እንጂ ሌላ ምን ሊባል ይችላል? በላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትና እና በሸዋ በሚገኘው የአዳዲ ማርያም ቤተ ክርስቲያን ኪነሕንጻ መካከል ያለው ፍጹም ተመሳሳይነት ምንጩ ምንድነው? ሊጠና፣ ሊነገር ልንማርበት ይገባል፡፡
በርግጥም ታሪካችን ትዝታችን ላይ የተጫነ ሸክም ሳይሆን የነፍስ መገለጥ ነው የሚያሰኘው የሕዝቦች ትሥሥር፣ ውህደት የሥልጣኔ መጋራትና መወራረስ ታሪክ መታወቁ መንፈስን ሃርነት ማውጣቱ ይመስለኛል፡፡
ጋዜጠኛ ዮናስ አየለ እንደጻፈው
ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ ከአሚኮ ጋር ያደረጉትን ቃለምልልስ አዳምጬ እንደጨረስኩ በቃለ ምልልሱ በርዕሰ ጉዳይ ደረጃ ጎልተው ከወጡ ዋና ዋና ጭብጦች መካከል አንዱ ነገረ ታሪክ እንደሆነ ተሰምቶኛል፡፡ ታሪክ-የሀገር ውስጥና የውጭ፤ የሩቅና የቅርብ ዘመን! ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቃለ ምልልሳቸው ያንጸባረቁትን ሚዛናዊና አምክኖአዊ የታሪክ እይታና ድምዳሜያቸውን አለማድነቅ ንፉግነት ነው፡፡ የአሥራ ዘጠነኛው ክፍለ ዘመን እንግሊዛዊ የታሪክ ጸሐፊና ፖለቲከኛ ሎርድ አክተን “History is not a burden on the memory but an illumination of the soul” ብሎ ሲጽፍ “ታሪክ የነፍስ መገለጥ እንጂ በትዝታ ላይ የተጫነ ሸክም አይደለም” ማለቱ ነበር፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቃለ ምልልሳቸው ያነሷቸው የታሪክ አንኳር ጉዳዮች እስከዛሬ ድረስ በሀገራችን የታሪክ አጻጻፍ(Historiography) እና በሕዝባዊ ትርክቶቻችን(በሚዲያዎችን ጭምር) በሚገባቸው ልክ ያልተወሱ፤ ቢወሱም ፈራ ተባ እየተባሉ የሚጠቀሱ፤ አለፍሲልም ባልተገባ የፖለቲካ እይታ ደንቃራ ተደርገው የተወሰዱ የታሪክ ግርዶሽ(eclipse of the history) ሆነው የኖሩ ስብራቶቻችን ነበሩ፡፡ ከነዚህ ቁልፍ ጉዳዮች መካከል ዋነኛዎቹ አንዱ የሕዝቦች ትስስር እና መስተጋብር ታሪክ ሲሆን ሌላኛው በአገረ መንግስት ምሥረታ ውስጥ የሸዋ ጂኦ-ስትራቴጂካዊ ሚናን የተመለከቱት ናቸው፡፡
በመጀመሪያ የአማራና የኦሮሞ ሕዝቦች በኩታ ገጠም ቀዬዎቻቸው እና የታሪክ እድል በፈጠረላቸው የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚና የባህል አጋጣሚዎች እንደሌሎች ማህበረሰቦች ሁሉ መጋባት መዋለዳቸው፤መተሳሰር መዋሀዳቸው ሀቅ የመሆኑን ያህል የታሪክ ጥናት እና የትርክቶቻችን ማጠንጠኛ አለመሆናቸው ይታወቃል፡፡ ከዚህ በባሰ ሁኔታ ደግሞ በነገሥታቱ መካከል የነበረው የፖለቲካ ጋብቻና የመሪዎቻችን ማህበራዊ መሠረት ጉዳይ ነውር እስኪመስል በእውነታው ልክ ሳይጠናና፣ሳይነገርለት ዘመናት አልፈዋል ፡፡ በሌላ በኩል በሸዋና አካባቢው ለረዥም ዘመን የኖሩ ሕዝቦች በአገረ መንግሥት ግንባታ ሂደት የተጫወቱት ሚናና የሚጋሩት ቀደምት የሥልጣኔ ባለቤትነት (ታሪክ ሰሪነት-Agency) ግጥምጥሞሽ በሀገር መሪ ደረጃ መወሳታቸው እጅግ ጉልህ ፋይዳ ያለው ጉዳይ ነው ፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቃለ ምልልሳቸው ያነሷቸው የታሪክ እውነታዎች ያለጥርጥር ታሪካችንንና የታሪክ ምልከታችንን ደጋግመን መመርምር እንዳለብን የሚያስገነዝቡና የወገንተኝነት ጥያቄ በሚነሳባቸው ሃይማኖታዊ የታሪክ ምንጮች እንኳን የተቀመጡ ገሃድ እውነታዎች ናቸው፡፡ መመርመር ለሚፈልግ አጥኚ እነዚህ የታሪክ እውነታዎች በየነገሥታቱ ዜና መዋዕሎች (የዐጼ አምደ ጽዮን፣ ዐጼ ሱስንዮስ፣የዐጼ ገላውዲዮስ፣ የዐጼ ሠርጸ ድንግል ወዘተ)፤ የሃይማኖት ሰነዶች፣ የታሪከ ነገሥት ቅጂዎች፣ ወደ ኢትዮጵያ መጥተው የነበሩ አውሮፓውያን ተጓዦችና ጸሐፊያን (ፍራንስስኮ አልቫሬዝ፣ ፔድሮ ፔዝ፣ ማኑኤል አልሜዳ፣ ጄሮኒሞ ሎቦ፣ ጀምስ ብሩስ፣ ኮንቲ ሮሲኒ ወዘተ ) መዝግበው በተውልን ሰነዶች ሰፍረው የምናገኛቸው፤ ከትውልድ ወደ ትውልድ ሲተላለፉ የኖሩ ቱባ መረጃዎች ናቸው፡፡
ፍራንሲስኮ አልቫሬዝ የተወልን የጽሑፍ ሰነድና ሌሎች ሀገርኛ የቃል መረጃ ምንጮች ዐፄ ልብነድንግል(1498-1532 ዓ.ም.) እንደ መሪ የአማራና የኦሮሞ ብቻ ሳይሆን ምናልባትም የሌሎች ሕዝቦችም ማህበራዊ ዳራ የነበራቸው ንጉሠ ነገሥት እንደሆኑ የሚያስረዱ ሲሆን አልቫሬዝ የንጉሱ የእናት ወንድም የነበሩት አጎታቸው ዶሪ ባህረ ነጋሽ ኦሮሞ እንደነበሩና ባህረ ነጋሽ ዶሪ ሲሞቱ ሥልጣኑ በቀጥታ ወደልጃቸው ቡሎ መሸጋገሩን ጭምር በአይኑ ያየውን ጽፏል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ በትኩረት መታየት የሚገባው ጉዳይ ስለዐጼ ልብነ ድንግል የጦር አዛዦች የተነገሩ የቃል መረጃዎች ናቸወ፡፡ ከእነዚህ መካከል የንጉሠ ነገሥቱ ሠራዊት የቦረንትቻ ባሕል ያውቅ እንደነበር በተክለጻዲቅ መኩሪያ መጻፉና ከዐጼ ልብነድንግል የጦር አዛዦች አንዱ የነበረው ቱሉ ደገልሀን በመራው ከኢማም አሕመድ ጋር የተካሄደ ጦርነት የዐጼው ጦር ሲያፈገፍግ ንጉሠ ነገሥቱ “ሁሉም ቢፈራ ቱሉ እንዴት ፈራ? ” ማለታቸው ስለሠራዊታቸው ሥብጥር የሚነግረን ነገር አለ፡፡
ኦቶማን ቱርኮችን እና የዘመኑ ተላላኪዎቻቸውን ለመዋጋት የንጉሠ ነገሥቱ ሠራዊት አንድ አካል ሆነው እስከ ኤርትራ ድረስ ዘምተው ስለነበሩ የኦሮሞ ተዋጊዎች ተጋድሎ የዐጼ ሠርጸድንግል(1542-1590 ዓ.ም.) ዜና መዋእል በግልጽ አስፍሯል፡፡ እነዚህ የኦሮሞና የሌሎች ሕዝቦች ተወላጅ ወታደሮች ትግራይ እንጢጮ አካባቢ ያካሄዱትን አውደ ውጊያ ዜና መዋዕሉ ይተርካል፡፡ ለመንግሥታቸውና ለሀገራቸው እስከባሕር ጠረፍ ድረስ ዘምተው ዋጋ መክፈላቸውም ተመዝግቧል፡፡ የዐጼ ሱስንዮስ(1607-1632 ዓ.ም.) ዜና መዋእል እና በዘመኑ ኢትዮጵያ መጥተው የነበሩ የአውሮፓ(የፖርቱጋል) ተጓዦች የጻፏቸው የመረጃ ምንጮች ንጉሠ ነገሥቱ ግንደበረት፣ሐምቦና አካባቢው ቤታቸው እንደነበር፤ አጎታቸው ለማሞ እንደሚባል፣ ወላጅ እናታቸው(ሐመልማል ወርቅ) የአዛዥ ኩሎ ልጅ የነበረች፤ የዚሁ የሐመልማል ወርቅ ጎሳ ተወላጅ የሆነ ቡኮ የተባለ ኦሮሞና ሠራዊቱ ለአባይ ቅርብ የሆነች ምዕራብ ሸዋ ላይ ዐጼ ሱስንዮስ ሲያገኙት የነበረውን ደስታና የፍቅሩን ጽናት ዜና መዋዕሉ ሳይሰስት ጽፎታል፡፡ ዐጼ ፋሲል(ከ1632 እስከ 1667 ዓ.ም.) አባቱ ሱስንዮስ እናቱ የወሎ ቃሉ ሰው(እቴጌ ሥልጣን ሞገሳ የሚል ስም የተሰጣት) እንደሆነች የታሪክ ምንጮች ያስረዱናል፡፡ በ1620ዎቹ ዓመታት ጀምሮ በኢትዮጵያ ይኖር የነበረው ፖርቱጋላዊ ቄስ ጄሮኒሞ ሎቦ ስለዐጼ ፋሲል እናትና ኦሮሞ ዘመዶቻቸው በአይን ምስክርነት የሚያውቀውን ጽፏል፡፡ የእቴጌ ሥልጣን ሞገሳ አያት ስለብዝሀ ሃይማኖት አስፈላጊነት የነበራቸውን ግልጽ ፖሊሲ ጭምር ሎቦ ዘግቦታል፡፡ የዐጼ በካፋ(1721-1730 ዓ.ም.) እና የዐጼ ኢዮአስ(1747-1761 ዓ.ም.) ጎንደር መቼም ለሕዝቦች ውህደትና ትስስር ጥሩ ማሳያ ነበረች፡፡ የየጁ ኦሮሞ ገዢ የነበረው የአሚቶ ሴት ልጅ ዝነኛዋ ውቢት ልጇ ዐጼ አዮአስ ነበር፡፡ ኢዮአስ ከኦሮሞ አጎቱ ከደጃች ሉቦ ጋር ሥልጣኑን በጎንደር እንዴት እንዳጸና፤ የቤተ መንግሥቱም የሥራ ቋንቋ አፋን ኦሮሞ እንደነበረ የንጉሠ ነገሥቱ ዜና መዋዕልና በጀምስ ብሩስ ቅጽ ሁለት መጽሀፍ የተመዘገቡ የታሪክ መረጃዎች ያስረዱናል፡፡
መነሻውን ወሎ በማድረግ ጎንደር ጸንቶ የኖረው የየጁ ሥርወ መንግሥት(ወረ ሼኮች) መሥራቾች የመርሳው አባ ጌትዬ፣ የልጃቸው ጓንጉል አባ ሴሩ እንዲሁም የልጅ ልጃቸው የራስ አሊ ጓንጉል(አሊ ትልቁ) ታሪክ በኢዮአስ ዜና መዋዕል፣ በጀምስ ብሩስ መጽሐፍና በሌሎች በርካታ ሰነዶች ታሪካቸው ተዘግቧል፡፡ በኋላ ላይ በሽፈራው በቀለ(ፕሮፌሰር) እና ሞላ ትኩዬ የቀረቡ ጥልቅ ጥናቶች ይህን እውነት በዝርዝር ያስረዱናል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቃለ ምልልሳቸው እንደጠቀሱት የእነዚህ መሪዎች የፖለቲካ ጋብቻ ታሪክ የሚያሳየን በሄዱበት አገር ሁሉ የሕዝቦች ትሥሥር እና የፖለቲካ ጋብቻ የኖረ ታሪካችን እና የጉልበታችን ምንጭ እንደነበረ ነው፡፡ በዳግማዊ ዐጼ ቴዎድሮስ ዘመን የተጻፉ የታሪክ ሰነዶች የወሎዋ ገዢ ወርቂቱ ወዳጆ(የማመዶች ሥርወ መንግሥት መሪ የኢማም አሊ አባ ቡላ ባለቤት) ንጉሥ ምኒልክ ከመቅደላ እስር ቤት እንዲያመልጡ ያደረጉ፤ አጃቢ ሠራዊት አሰማርተው ምኒልክን እስከሸዋ የሸኙ እንደነበሩ በዋናነት ከጸሓፌ ትእዛዝ ገብረ ሥላሴ ታሪከ ዘመን ዘ ዳግማዊ ምኒልክ ዜና መዋዕል እና በመቅደላ አምባ እስር ላይ የነበሩ አውሮፓውያን ከጻፏቸው መረጃዎች እንረዳለን፡፡
ሥልጣኔዎቻችን ሁሉ ተደምረን ያሳካናቸው እንደሆነ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቃለ ምልልሳቸው አንስተዋል፡፡ የዐድዋ ዘመቻና ድሉ ለዚህ አንዱ ማሳያ እንደሆነ ተጨባጭ የታሪክ ምንጮች ያስረዱናል፡፡ በ1888 ዓ.ም. ለዓድዋ ዘመቻ ከመላው ኢትዮጵያ የተመመው ሠረዊት ወፍላ ላይ የነበረው ሠልፍ የንጉሠ ነገሥቱ ዜና መዋዕል እንኳን እንዲህ ይገልጸዋል፡፡ “የመኳንንቱ የጦር መሣሪያ፣ወርቁ፣ ጣፋ፣ ብሩ፣ ሙጣው፣ ጫሜው፣ ሎሚታውና ኩፊታው፣ ከሌቻው፣ ወርቅ ለምዱ እንደጸሐይ ሲያበራ ዋለ፡፡” እንደጸሐይ የበራውን ሕብረ ባሕልና ሕብረ ማንነት ትርክቶቻችን በልኩ አጉልተው ያውቃሉ?
ሸዋና አካባቢው(ወሎን ጨምሮ) እንደ አንድ ጂዞ ስትራቴጂ ሥፍራ የሕዝቦች ውህደትና ትስስር መሠረት ሆኖት የመልክዓ ምድር መገኛው ለግብርና እና ለውጭ ንግድ የተመቸ በመሆኑ በኢትዮጵያ አገረ መንግሥት ግንባታ ታሪክ ውስጥ ቁልፍ ቦታ ይዞ መኖሩን ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቃለ ምልልሳቸው መግቢያ አስታውሰውናል፡፡ ሸዋና አካባቢው ከመንግሥታት ምስረታ ጋር በተገናኘ ከዘጠነኛው አንስቶ እስካሁን ያለው ረዥም የታሪክ ጉዞ በርግጥም ሊነገር፣ ሊተነተን የአደባባይ ትርክት አካል ሊደረግ የሚገባው እውነት ነው፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከሸዋ ሡልጣኔት ምስረታ( እ.አ..አ.896 ዓ.ም.) እስከ ዓድዋ ድል(1888 ዓ.ም.) ሥላወሷቸው የአርጎባ(የወላስማ/ወሊ አስማ ሥርወ መንግሥት)፣ የአማራ(ሰለሞናዊ ሥርወ መንግሥት)፣ ኦሮሞ(ቱለማው በተለይ)፣ወርጂ፣ ጉራጌ፣ ጋፋት፣ ወዘተ ሕዝቦች ትስስርም ይሁን የፖለቲካ ጋብቻ የተመለከተ ታሪክ ከበቂ በላይ የታሪክ ማስረጃ ምንጮች ቢኖሩንም በታሪክ ግርዶሹ ምክንያት የወል ትርክት አካል መሆን አልቻለም፡፡
ኤንሪኮ ቼሩሊ ከሐረር አግኝቶ ያሳተመው በአረብኛ የተጻፈው የሸዋ ሡልጣኔት ዜና መዋዕል እንደሚያመለክተው ሡልጣኔቱን እ.አ.አ. በ896/7 የመሰረቱት የማህዙሚ ጎሳ አባላት ናቸው፡፡ መንግሥታቸውም ከ9ኛው እስከ 13ኛው ክፍለ ዘመን ድረስ በተከታታይ በገዙ አሥራ አራት ሱልጣኖች እንደጸና የታሪክ መረጃ ምንጮች ያመለክታሉ፡፡ የሸዋ ሙስሊም ሡልጣኔቱ መቀመጫ ከተማ ከአዲስ አበባ በስተሰሜን ምሥራቅ 70 ኪሎ ሜትር ላይ የምትገኝ ወለላ የተባለች ሥፍራ እንደነበረች የጆርጅ ደብሊው ቢ ሀንቲንግፎርድ(1989) ጥናት ያመለክታል፡፡ የማህዙሚ ሥርወ መንግሥት ከመጨረሻዎቹ መሪዎች አንዱ የነበረው ሡልጣን ድልመራህ ወርጂዎች የይኖሩበት በነበረው አካባቢ በ1270ዎቹ በነበረ የርስ በርስ ጦርነት ድል ሳይቀናው ሲቀር ሕይወቱን ለማትረፍ ዐጼ(የአማራ ገዥ?) እንደሄደ ይህው የአረብኛ ዜና መዋእል ያስረዳል፡፡ የማህዙሚዎች የሸዋ ሡልጣኔት የተተካው በዋናነት የአርጎባዎች አገር በሆነው ይፋት(ዊፋት) ላይ በወላስማዎች ነበር፡፡ ወላስማዎች ከአጎራባቾቻው ጋር እየተጋቡ፣ እየተስማሙም እየተጋጩም የይፋት ሡልጣኔትን ከ13ኛው እስከ 15ኛው ክፍለ ዘመን ከሸዋ እስከ ምሥራቃዊ የኢትዮጵያ ጠረፍ እንዳስተዳደሩ ስፍር ቁጥር የሌለው የሰነድ( የኢብን ካልዱን ተማሪ የነበረው አል ማቅሪዚ ጽሑፍ- ኪታብ አል ኢልማም)፣ የአርኪዮሎጂና የቃል መረጃ ምንጮች አሉ፡፡
መነሻውን ሰሜን ሸዋ እና ደቡብ ወሎ ያደረገው የክርስቲያኑ ሰሎሞናዊ ሥርወ መንግሥት በአካባቢው ያሉ ሕዝቦች ተዋህደው ከ13ኛው ክፍለ ዘመን ጀምሮ በጋራ የመሠረቱት እንደሆነ አያጠያይቅም፡፡ አማራዎች፤ አርጎባዎች፣ ወርጂዎች፣ ጋፋቶች፣ ጉራጌዎች እና ኦሮሞዎች፣ አፋሮች፣ ሐረሪዎች ወዘተ በዚህ የሸዋ መንግሥታት የተጽዕኖ ምህዳር(Orbit) ውስጥ እንደሚገኙ ዜና መዋእሎች፣ የሃይማኖት ሰነዶች፣ የአርኪዮሎጂ ማስረጃዎች ከትውልድ ወደ ትውልድ ሲተላለፉ የኖሩ የቃል መረጃ ምንጮች ያመለክታሉ፡፡ ለምሳሌ ታደሠ ታምራት(ፕሮፌሠር) ከ13ኛው እስከ 16ኛው ክፍለ ዘመን የቤተ ክርስቲያንና መንግሥትን ግንኙነት ታሪክ ባጠኑበት መጽሐፋቸው የገላንና ያያ ሰዎች ሸዋ ውስጥ በ13ኛው ክፍለ ዘመን በኦዳ ዛፍ (ኮቢል የሚባል ዋርካ) ሥር ሃይማኖታዊ ሥርዓት ይፈጽሙ እንደነበር ገድለ አቡነ ቀውስጦስን ጠቅሰው ጽፈዋል(ገጽ 184)፡፡ ሸዋ የባለ ብዙ ማንነት ሕዝቦች ሀገር ከመሆኗ ባሻገር በ16ኛው ክፍለ ዘመን የተከናወኑ ዐበይት ጉዳዮች ላይ መረጃ የተወልን መነኩሴው አባ ባህሪይ እንደገለጸው “ሸዋ የመንግሥት ሀገር ነች” (ገጽ 130)፡፡ በየዘመናቱ ከሸዋ የተነሱ የፖለቲካ ኃይሎች፣ ፈረሰኛ ሠራዊታቸውን ይዘው በሰሜን እስከ ኤርትራ(በዐጼ ሠርጸ ድንግል ዘመን- የኤርትራዋ ባሬንቱ የዚህ የታሪክ ሂደት ውርስ አይደለችም ማለት አይቻልም፡፡) በምሥራቅ እስከ ዘይላ(ከዐጼ አምደጽዮን እስከ ገላውዲዮስ ዘመን)፣ በምዕራብ እስከ ሱዳን ፋዞግሊ(ዐጼ ሱስንዮስ ዘመን) በደቡብ እስከ ሞያሌ ተንቀሳቅሰው በአገረ መንግሥት ግንባታ ሂደት ውስጥ ቁልፍ ሚና ተጫተዋል፡፡
እነዚህ የሸዋ እና አካባቢው ሕዝቦችና ገዢዎች ትልቁን ንቅናቄያቸውን ያደረጉት ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን እንደሆነ ይታወቃል፡፡ ዐጼ ምኒልክና ራስ ጎበና ዳጬ የቱለማ ኦሮሞ፤ የሸዋ አማራ እና የሌሎችም ውህድ የሆነ ጦራቸውን አዝምተው ወሎ ወግተው ወረኢሉን የመንሥታቸው መቀመጫ ያደረጉት አርሲ፣ወለጋ፣ከሐረር ከመዝመታቸው በፊት ነበር፡፡ የመጫ ኦሮሞ ተወላጁን የጎጃሙን ንጉስ ተክለሃይማኖት(አዳል ተሰማ) በቱለማው መሪ ራስ ጎበና ዳጪ እምባቦ ላይ ያስገበሩት የጂኦ ፖለቲካዊ እና የሕዝቦች ትስስር እድሎች ጉልበት ፈጥሮላቸው፤ ኃይል አጎናጽፏቸው እንጂ በአጋጣሚ አይደለም፡፡ በርግጥ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የፖለቲካችን ደንቃራነት የፈጠረውን የታሪክ ግርዶሽ ያሸነፉ ፋና ወጊ ጥናቾች መውጣት ጀምረዋል፡፡ አንዱ “Invisible Actors: The Oromo and the Creation of Modern Ethiopia(1855-1913)” በሚል ርዕስ በብሪያን ጀምስ ዬትስ(2002) በኤሊኖይስ ዩኒቨርሲቲ ከተጠናው እጅግ ጠቃሚ የዶክትሬት ዲግሪ ማሟያ ጥናት ሲሆን ሌላው የደቻሳ አበበ(ዶ/ር) ጎበና ወታደራዊና ፖለቲካዊ ሕይወት ነው፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቃለ ምልልሳቸው የዘመናዊት ኢትዮጵያን እውን መሆን ያለ ምኒልክና ያለ ጎበና እንደማይታሰብ ሲጠቅሱ ይህንን እውነታ ማጉላታቸው ይመስለኛል፡፡
የሕዝቦች ትስስርና የፖለቲካ ጋብቻ በአማራና በኦሮሞ ሕዝብ መስተጋብር ብቻ የታጠረ አልነበረም-ሊሆንም አይችልም፡፡ የኢትዮጵያ ሕዝብ ባህልና ሥልጣኔ መጋመዱ ረቂቅ ነው፡፡ ከጥንታዊ አክሱም ዘመን ጀምሮ በዝነኞቹ የአክሱም መቃብር ሀውልቶች እና በላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናት ላይ ከምናገኛቸው የኪነ ሕንጻ ትእምርቶች(Symbols) መካከል የውሸት በሮች (False Doors) እና የውሸት መስኮቶች(False windows) የሙታን መንፈስ(ኤከራ) መመላለሻ እንደሆኑ በጥናት የተረጋገጠ ነው (ቢትራይስ ፕሌይን Annales d'Éthiopie 1965) ፡፡ ይህ የኤከራዎች መመላለስና የመነጋገር ባህል እና እምነት ከደቡባዊ ግብጽ አንስቶ እስከ ሰሜን ኬንያ ድረስ በሚኖሩ የኩሽ ሕዝቦች በሰፊው የሚታወቅ ረዥም ዘመን ያስቆጠረ ልምምድ ነው፡፡
ሌላው በልኩ ያልተጠና እና በትርክቶቻችን ውስጥ ትኩረት ያልተሰጠው በሕዝቦች መካከል ያለ ሥልጣኔ ትስስር ታሪክ የእያንዳዱን የዛግዌ ነገሥታት የሥልጣን ዘመናትን የተመለከተ ነው፡፡ ከታሪክ ነገሥት፣ ከልዩ ልዩ ዜና መዋዕሎች፣ ከፖርቱጋል ተጓዦች(ፓኤዝና አልሜዳ) ከብሪቲሽ ሙዝየም እንዲሁም ከኮንቲ ሮሲኒ የተገኙት ምንጮች የሚረጋግጡት የሁሉም የዛግዌ ዐጼዎች( ከአንድ ሁለቱ በስተቀር) የሥልጣን ዘመን 40፤40 ዓመታት ነበር፡፡ ይህ ጉዳይ በኦሮሞ የገዳ ሥርዓት የአንድ ትውልድ የሥልጣን ዑደት ጋር አንድ አይነት የሆነው በአጋጣሚ ነው ወይስ ዛግዌዎች እና ኦሮሞዎች የኩሽ ሕዝቦች በመሆናቸው ቀዳሚ ከሆነው የጋራ ሥልጣኔያቸው የሚቀዳ የአስተዳደር ሥርዓት ነው? እነዚህስ ሀቆች የወል ትርክቶቻችን መመሆን አለመቻላቸው በፖለቲካ ደንቃራነት የተፈጠረ የታሪክ ግርዶሽ(eclipse of history) እንጂ ሌላ ምን ሊባል ይችላል? በላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትና እና በሸዋ በሚገኘው የአዳዲ ማርያም ቤተ ክርስቲያን ኪነሕንጻ መካከል ያለው ፍጹም ተመሳሳይነት ምንጩ ምንድነው? ሊጠና፣ ሊነገር ልንማርበት ይገባል፡፡
በርግጥም ታሪካችን ትዝታችን ላይ የተጫነ ሸክም ሳይሆን የነፍስ መገለጥ ነው የሚያሰኘው የሕዝቦች ትሥሥር፣ ውህደት የሥልጣኔ መጋራትና መወራረስ ታሪክ መታወቁ መንፈስን ሃርነት ማውጣቱ ይመስለኛል፡፡
4 days ago
እነሆ ''ተስፋን እንትከል'''
#ethiopia | "ዛፍ ለመትከል የተሻለው ጊዜ ከ20 ዓመታት በፊት ነበር፤ ሁለተኛው የተሻለው ጊዜ ደግሞ አሁን ነው" እንደሚባለው ሁሉ፣ ዛፍ መትከል ተስፋን መትከል በመሆኑና ሕይወታችንን ሰናይ ለማድረግ ደኖቻችንን ማልማት አስፈላጊ ነው።
በዓለም አቀፍ ደረጃ የምድራችን 31 ከመቶ የሚሆነው አካል በደን የተሸፈነ ቢሆንም፣ የደን ሽፋን በየጊዜው እያቆለቆለ በመምጣቱ እስከ እ.ኤ.አ 2030 ድረስ 1 ትሪሊዮን ዛፎችን ለመትከልና ለመንከባከብ እንቅስቃሴ እየተደረገ ይገኛል።
በሀገራችን በ20ኛው ክፍለ ዘመን መጀመሪያ ላይ 40 ከመቶ የነበረው የደን ሽፋን ለእርሻ መሬት መስፋፋት ሲባል ተመንጥሮ ወደ 2 ከመቶ ወርዶ የነበረ ቢሆንም፣ ባለፉት አምስት ዓመታት በተደረገው ከፍተኛ ጥረት የደን ሽፋኑ በ2023 ወደ 23.6 ከመቶ ማደግ ችሏል።
በዚህ መነሻም የፌዴራል ቱሪዝም ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሆሳዕና ከተማ የክረምት ወራት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት አካል የሆኑ ሀገራዊና ማህበራዊ ልማቶችን አከናውኗል።
በኢንስቲትዩቱ "ተስፋን እንተክላለን" በሚል ሀገራዊ ራዕይ የአንድ ጀንበር የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በማካሄድ ከአካባቢው ማህበረሰብ ጋር በመተባበር በቦቢቾ ቀበሌ ለምግብነትና ለአካባቢ ጥበቃ የሚውሉ 5 ሺህ ችግኞችን ተክሏል።
ከችግኝ ተከላው ጎን ለጎንም በጀሎ ናረሞ ቀበሌ "የዛሬ ህፃናት የነገ ተስፋ ናቸው" በሚል መሪ ቃል የነገ ሀገር ተረካቢ ህፃናትን አእምሯዊ እድገት ለመደገፍ የሚያስችል ዘመናዊ የመዋዕለ ህፃናት ግንባታ መሠረት ድንጋይ አኖሯል።
በዚሁ መርሃ ግብር ላይ ኢንስቲትዩቱ ከግንባታው ባሻገር ለአንድ ሺህ ተማሪዎች የሚሆን የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ ለሆሳዕና ከተማ ከንቲባ ለአቶ ሳሙኤል ሽጉጤ እና ለትምህርት ጽሕፈት ቤት ሃላፊው አስረክቧል።
የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር አቶ ጌታቸው ነጋሽ የክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ሀገራዊ አንድነትን እንደሚያጠናክር ገልጸው፣ ደረጃውን የጠበቀ እና በቴክኖሎጂ የታገዘ የትምህርት ቁሳቁስ የሚሟላለት ይህ መዋዕለ ህፃናት በአጭር ጊዜ ውስጥ ተገንብቶ ለአገልግሎት እንዲበቃ አስፈላጊው ክትትል እንደሚደረግ አረጋግጠዋል።
የሆሳዕና ከተማ ከንቲባ አቶ ሳሙኤል ሽጉጤ እና የአካባቢው የሀገር ሽማግሌዎች ለተከናወኑት የልማትና የበጎ አድራጎት ሥራዎች ለኢንስቲትዩቱ አመራሮችና ሠራተኞች ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
ለ Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን) ሚዲያና ኮሙኒኬሽን
ያፌት ገ/ህይወት
ከሀዲያ ዞን ፤ ሆሳዕና
#ethiopia | "ዛፍ ለመትከል የተሻለው ጊዜ ከ20 ዓመታት በፊት ነበር፤ ሁለተኛው የተሻለው ጊዜ ደግሞ አሁን ነው" እንደሚባለው ሁሉ፣ ዛፍ መትከል ተስፋን መትከል በመሆኑና ሕይወታችንን ሰናይ ለማድረግ ደኖቻችንን ማልማት አስፈላጊ ነው።
በዓለም አቀፍ ደረጃ የምድራችን 31 ከመቶ የሚሆነው አካል በደን የተሸፈነ ቢሆንም፣ የደን ሽፋን በየጊዜው እያቆለቆለ በመምጣቱ እስከ እ.ኤ.አ 2030 ድረስ 1 ትሪሊዮን ዛፎችን ለመትከልና ለመንከባከብ እንቅስቃሴ እየተደረገ ይገኛል።
በሀገራችን በ20ኛው ክፍለ ዘመን መጀመሪያ ላይ 40 ከመቶ የነበረው የደን ሽፋን ለእርሻ መሬት መስፋፋት ሲባል ተመንጥሮ ወደ 2 ከመቶ ወርዶ የነበረ ቢሆንም፣ ባለፉት አምስት ዓመታት በተደረገው ከፍተኛ ጥረት የደን ሽፋኑ በ2023 ወደ 23.6 ከመቶ ማደግ ችሏል።
በዚህ መነሻም የፌዴራል ቱሪዝም ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሆሳዕና ከተማ የክረምት ወራት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት አካል የሆኑ ሀገራዊና ማህበራዊ ልማቶችን አከናውኗል።
በኢንስቲትዩቱ "ተስፋን እንተክላለን" በሚል ሀገራዊ ራዕይ የአንድ ጀንበር የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በማካሄድ ከአካባቢው ማህበረሰብ ጋር በመተባበር በቦቢቾ ቀበሌ ለምግብነትና ለአካባቢ ጥበቃ የሚውሉ 5 ሺህ ችግኞችን ተክሏል።
ከችግኝ ተከላው ጎን ለጎንም በጀሎ ናረሞ ቀበሌ "የዛሬ ህፃናት የነገ ተስፋ ናቸው" በሚል መሪ ቃል የነገ ሀገር ተረካቢ ህፃናትን አእምሯዊ እድገት ለመደገፍ የሚያስችል ዘመናዊ የመዋዕለ ህፃናት ግንባታ መሠረት ድንጋይ አኖሯል።
በዚሁ መርሃ ግብር ላይ ኢንስቲትዩቱ ከግንባታው ባሻገር ለአንድ ሺህ ተማሪዎች የሚሆን የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ ለሆሳዕና ከተማ ከንቲባ ለአቶ ሳሙኤል ሽጉጤ እና ለትምህርት ጽሕፈት ቤት ሃላፊው አስረክቧል።
የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር አቶ ጌታቸው ነጋሽ የክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ሀገራዊ አንድነትን እንደሚያጠናክር ገልጸው፣ ደረጃውን የጠበቀ እና በቴክኖሎጂ የታገዘ የትምህርት ቁሳቁስ የሚሟላለት ይህ መዋዕለ ህፃናት በአጭር ጊዜ ውስጥ ተገንብቶ ለአገልግሎት እንዲበቃ አስፈላጊው ክትትል እንደሚደረግ አረጋግጠዋል።
የሆሳዕና ከተማ ከንቲባ አቶ ሳሙኤል ሽጉጤ እና የአካባቢው የሀገር ሽማግሌዎች ለተከናወኑት የልማትና የበጎ አድራጎት ሥራዎች ለኢንስቲትዩቱ አመራሮችና ሠራተኞች ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
ለ Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን) ሚዲያና ኮሙኒኬሽን
ያፌት ገ/ህይወት
ከሀዲያ ዞን ፤ ሆሳዕና
4 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት ወዲህ የተገመተውን "እጅግ ግዙፍ ጥቃት" በኢራን ላይ ከመፈጸም ማገዳቸውን ተከትሎ፣ ከፊታችን ሰኞ ጀምሮ "በድርድር መልክ" የሚካሄድ አዲስ ውይይት እንደሚጀምሩ አስታውቀዋል። ይሁን እንጂ ኢራን ፕሬዝዳንቱ ለዲፕሎማሲያዊ መፍትሄ ያላቸውን እውነተኛ ቁርጠኝነት በተመለከተ ከፍተኛ ጥርጣሬ አላት።
በኩዊንሲ ኢንስቲትዩት ተመራማሪ የሆኑት ትሪታ ፓርሲ እንደተናገሩት፣ የዲፕሎማሲው ጥረት ስኬታማ እንዲሆን አሜሪካ እና ኢራን ከሆርሙዝ ስትሬት ባሻገር በሌሎች ሰፋፊ ጉዳዮች ላይ ስምምነት ላይ መድረስ አለባቸው።
የሆርሙዝ የውሃ መስመር ጉዳይ አንዱ እና ወሳኙ አካል መሆኑን የጠቀሱት ፓርሲ፣ ባለፈው ሰኔ ወር በአሜሪካ እና በኢራን መካከል የተፈረመው የመግባቢያ ሰነድ በመላው ቀጠናው ተኩስ አቁም እንዲደረግ የሚጠይቅ እንደነበር አስታውሰዋል። ነገር ግን እስራኤል በሊባኖስ እና በጋዛ ላይ የምትፈጽመውን ጥቃት መቀጠሏ የቀጠናውን የተኩስ አቁም ጥያቄ የሚጥስ በመሆኑ፣ ይህ ሰነድ ለታደሰው ዲፕሎማሲ መነሻ የሚሆን ከሆነ "ወደ ነበርንበት አልፎም ወደ ከፋ ሁኔታ ልንመለስ እንችላለን" ሲሉ ሞግተዋል።
ያም ሆኖ ሁለቱም ወገኖች ዲፕሎማሲያዊ ጥረቱ እንዲከሽፍ መፍቀድ እንደሌለባቸው ያስጠነቀቁት ተመራማሪው፣ ምክንያቱም በመጨረሻ የሚኖረው ሌላኛው አማራጭ እጅግ አውዳሚ መሆኑን አስገንዝበዋል።
አክለውም ፕሬዝዳንት ትራምፕ በእርግጥ "ምንም ዓይነት ወታደራዊ አማራጭ እንደሌላቸው" ራሳቸውን እስካላሳመኑ ድረስ ለዘላቂ ስምምነት ይቆማሉ ብላ ቴህራን ስለማታምን፣ ለዲፕሎማሲ ያላቸውን ታማኝነት አሁንም በጥርጣሬ እንደምትመለከተው ፓርሲ አስረድተዋል።
በኩዊንሲ ኢንስቲትዩት ተመራማሪ የሆኑት ትሪታ ፓርሲ እንደተናገሩት፣ የዲፕሎማሲው ጥረት ስኬታማ እንዲሆን አሜሪካ እና ኢራን ከሆርሙዝ ስትሬት ባሻገር በሌሎች ሰፋፊ ጉዳዮች ላይ ስምምነት ላይ መድረስ አለባቸው።
የሆርሙዝ የውሃ መስመር ጉዳይ አንዱ እና ወሳኙ አካል መሆኑን የጠቀሱት ፓርሲ፣ ባለፈው ሰኔ ወር በአሜሪካ እና በኢራን መካከል የተፈረመው የመግባቢያ ሰነድ በመላው ቀጠናው ተኩስ አቁም እንዲደረግ የሚጠይቅ እንደነበር አስታውሰዋል። ነገር ግን እስራኤል በሊባኖስ እና በጋዛ ላይ የምትፈጽመውን ጥቃት መቀጠሏ የቀጠናውን የተኩስ አቁም ጥያቄ የሚጥስ በመሆኑ፣ ይህ ሰነድ ለታደሰው ዲፕሎማሲ መነሻ የሚሆን ከሆነ "ወደ ነበርንበት አልፎም ወደ ከፋ ሁኔታ ልንመለስ እንችላለን" ሲሉ ሞግተዋል።
ያም ሆኖ ሁለቱም ወገኖች ዲፕሎማሲያዊ ጥረቱ እንዲከሽፍ መፍቀድ እንደሌለባቸው ያስጠነቀቁት ተመራማሪው፣ ምክንያቱም በመጨረሻ የሚኖረው ሌላኛው አማራጭ እጅግ አውዳሚ መሆኑን አስገንዝበዋል።
አክለውም ፕሬዝዳንት ትራምፕ በእርግጥ "ምንም ዓይነት ወታደራዊ አማራጭ እንደሌላቸው" ራሳቸውን እስካላሳመኑ ድረስ ለዘላቂ ስምምነት ይቆማሉ ብላ ቴህራን ስለማታምን፣ ለዲፕሎማሲ ያላቸውን ታማኝነት አሁንም በጥርጣሬ እንደምትመለከተው ፓርሲ አስረድተዋል።
5 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የፖለቲካ ትንታኔ አቅራቢው ሬኔ ሌፎርት በኢትዮጵያ እና ሱዳን ድንበር አካባቢ ተቀሰቀሰ ስለተባለው ትጥቃዊ ግጭት የሚወጡ ዘገባዎችን ለመተንተን ከፍተኛ ጥንቃቄ ማድረግ እንደሚያስፈልግ አሳስበዋል። ተንታኙ በኤክስ ገጻቸው ባሰፈሩት ጽሁፍ፣ ለዚህ ጥንቃቄ በምክንያትነት ካነሷቸው ነጥቦች መካከል የፌደራል መንግስቱ (አዲስ አበባ) ሙሉ በሙሉ ዝምታን መምረጡ እና የህወሓት መረጃዎች ተዓማኒነት አጠያያቂ መሆኑ ይገኙበታል።
አያይዘውም ውጊያው እንደተዘገበው በሸረሪና አካባቢ የጀመረ ከሆነ፣ በግጭቱ የተሳተፉት ኃይሎች የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት (ENDF)፣ አዲስ አበባን የሚደግፉ የአማራ ሚሊሻዎች እና አጠቃላይ የትግራይ መከላከያ ኃይልን (TDF) ሳያካትት የትግራይ ሰራዊት 'አርሚ 70' ኮር ብቻ ሊሆኑ እንደሚችሉ አመላክተዋል። ይሁን እንጂ የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት በውጊያው ውስጥ በትክክል ስለመሳተፉ እስካሁን የታወቀ ነገር እንደሌለ እና ግልጽ ያልሆነ ጉዳይ መሆኑን ገልጸዋል።
ሬኔ ሌፎርት አሁን ያለውን ሁኔታ በተመለከተ ሁለት ሊሆኑ የሚችሉ ግምቶችን አስቀምጠዋል። የመጀመሪያው፣ አሜሪካ እና የአውሮፓ ህብረትን ጨምሮ ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ግጭቱን ለመከላከል ከፍተኛ ጫና እያደረጉ ቢሆንም፣ ይህ ክስተት በመላው የአፍሪካ ቀንድ ሊስፋፋ የሚችል አውዳሚ ጦርነት መነሻ ሊሆን እንደሚችል ነው።
ሁለተኛው ግምት ደግሞ "ያዙኝ ካለበለዚያ ጥፋት አደርሳለሁ" በሚል ስሌት፣ ሸምጋዮችን በማስገደድ የተፈጠረውን የፖለቲካ ማነቆ በድርድር ለመፍታት የተተኮሰ የማስጠንቀቂያ ተኩስ ሊሆን እንደሚችል ነው። ሆኖም ክስተቱ ከሁለቱ የትኛው እንደሆነ በእርግጠኝነት ለመናገር አሁንም በጣም ገና መሆኑን ትንታኔያቸው ያሳያል።
አያይዘውም ውጊያው እንደተዘገበው በሸረሪና አካባቢ የጀመረ ከሆነ፣ በግጭቱ የተሳተፉት ኃይሎች የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት (ENDF)፣ አዲስ አበባን የሚደግፉ የአማራ ሚሊሻዎች እና አጠቃላይ የትግራይ መከላከያ ኃይልን (TDF) ሳያካትት የትግራይ ሰራዊት 'አርሚ 70' ኮር ብቻ ሊሆኑ እንደሚችሉ አመላክተዋል። ይሁን እንጂ የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት በውጊያው ውስጥ በትክክል ስለመሳተፉ እስካሁን የታወቀ ነገር እንደሌለ እና ግልጽ ያልሆነ ጉዳይ መሆኑን ገልጸዋል።
ሬኔ ሌፎርት አሁን ያለውን ሁኔታ በተመለከተ ሁለት ሊሆኑ የሚችሉ ግምቶችን አስቀምጠዋል። የመጀመሪያው፣ አሜሪካ እና የአውሮፓ ህብረትን ጨምሮ ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ግጭቱን ለመከላከል ከፍተኛ ጫና እያደረጉ ቢሆንም፣ ይህ ክስተት በመላው የአፍሪካ ቀንድ ሊስፋፋ የሚችል አውዳሚ ጦርነት መነሻ ሊሆን እንደሚችል ነው።
ሁለተኛው ግምት ደግሞ "ያዙኝ ካለበለዚያ ጥፋት አደርሳለሁ" በሚል ስሌት፣ ሸምጋዮችን በማስገደድ የተፈጠረውን የፖለቲካ ማነቆ በድርድር ለመፍታት የተተኮሰ የማስጠንቀቂያ ተኩስ ሊሆን እንደሚችል ነው። ሆኖም ክስተቱ ከሁለቱ የትኛው እንደሆነ በእርግጠኝነት ለመናገር አሁንም በጣም ገና መሆኑን ትንታኔያቸው ያሳያል።
5 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና ዳሰሳ) የሶማሌላንድ የሀገርነት ጥያቄ እና አለም አቀፍ እውቅና የማግኘት ፍላጎት በዋናነት የተመሰረተው በቅኝ ግዛት ወቅት በነበራት ግልጽ ድንበር፣ እ.ኤ.አ. በ1960 ለተወሰኑ ቀናት አግኝታው በነበረው ነጻነት እና በ1991 ያወጀችው ነጻነት አዲስ የመገንጠል ጥያቄ ሳይሆን የነበረን ሉዓላዊነት የመመለስ እርምጃ ነው በሚለው መከራከሪያ ላይ ነው። እንግሊዝ ከ1884 እስከ 1886 በሰሜን ሶማሊያ ከሚገኙ የጎሳ መሪዎች ጋር ባደረገችው የስምምነት ውል መሰረት የሶማሌላንድን ግዛት የመሰረተች ሲሆን፣ የውጭ ድንበሮቿም ከፈረንሳይ፣ ጣሊያን እና ኢትዮጵያ ጋር በተደረጉ አለም አቀፍ ስምምነቶች የተከለሉ ነበሩ። ሰኔ 26 ቀን 1960 ከእንግሊዝ ቅኝ ግዛት ነጻነቷን የተቀዳጀችው ሶማሌላንድ፣ ከአምስት ቀናት በኋላ በፈቃደኝነት ከጣሊያን ሶማሊያ ጋር በመዋሃድ የሶማሊያ ሪፐብሊክን መስርታለች። ይሁን እንጂ የሶማሊያ ማዕከላዊ መንግስት በ1991 መውደቁን ተከትሎ፣ ሶማሌላንድ ከውህደቱ በፊት ወደ ነበራት ነጻነት መመለሷን በማወጅ የ1960ዋን ግዛቷን ይዛለች።
የሶማሌላንድ ዋነኛ የህግ መከራከሪያ አዲስ ነጻ የሚወጡ ሀገራት በቅኝ ግዛት ወቅት የነበራቸውን ድንበር ጠብቀው ሊቀጥሉ ይገባል የሚለው መርህ ነው። የአፍሪካ አንድነት ድርጅት በ1964ቱ የካይሮ ውሳኔው እንዲሁም የአፍሪካ ህብረት የመመስረቻ ሰነዱ ላይ አባል ሀገራት በነጻነት ጊዜ የነበራቸውን ድንበር ሊያከብሩ እንደሚገባ አስፍረዋል። በመሆኑም ሶማሌላንድ አለም አቀፍ እውቅና ማግኘቷ የቅኝ ግዛት ድንበርን ከመጠበቅ ባለፈ አዲስ ድንበር የማካለል ስራ አይደለም በማለት ትከራከራለች። አቋሟም ከዚህ ቀደም ሉዓላዊ ሀገር እንደነበረች፣ የ1960ውን ውህደት በራሷ ፈቃድ እንደፈጸመች እና የ1991ዱ እርምጃዋም የከሸፈን ውህደት ማፍረስ እንጂ አዲስ ግዛትን ከሶማሊያ መገንጠል አይደለም በሚሉ ሶስት ምሶሶዎች ላይ የቆመ ነው። ይህ አቀራረብ ሶማሌላንድን ምንም አይነት የቅኝ ግዛት ወይም አለም አቀፍ ድንበር መሰረት ከሌላቸው የመገንጠል ጥያቄዎች የተለየች ያደርጋታል።
የሶማሌላንድን ሁኔታ ከኤርትራ ጋር ማነጻጸር የጉዳዩን የዲፕሎማሲ ውስብስብነት በደንብ ያሳያል። ሁለቱም ግዛቶች የተለየ የቅኝ ግዛት ታሪክ፣ ከማዕከላዊ መንግስት ጋር የተደረገ የትጥቅ ትግል እና ከ1991 በኋላ ውጤታማ የሆነ ራስን በራስ የማስተዳደር ልምድ አላቸው። ይሁን እንጂ የኤርትራ የነጻነት ጥያቄ የኢትዮጵያን የሽግግር መንግስት ፈቃድ እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የህዝበ ውሳኔ ታዛቢነትን በማግኘቱ ፈጣን አለም አቀፍ እውቅናን ሊያጎናጽፋት ችሏል። በሶማሌላንድ በኩል ግን ጠንካራ ተቋማትን መገንባት እና ህዝበ ውሳኔ ማካሄድ ብትችልም፣ ከሶማሊያ መንግስት የተገኘ ስምምነትም ሆነ እንደ ኤርትራው አይነት አለም አቀፍ ድጋፍ ባለማግኘቷ የዲፕሎማሲ እውቅናው ሊዘገይባት ችሏል። ይህ የሚያሳየው ውጤታማ አስተዳደር እና ታሪካዊ ድንበር መኖር ብቻውን በቂ እንዳልሆነ እና እውቅና ማግኘት በስምምነት፣ በቀጠናዊ ፖለቲካ እና በዲፕሎማሲያዊ ድጋፍ ላይ በእጅጉ የተመሰረተ መሆኑን ነው።
የአፍሪካ ህብረት በ2005 ወደ አካባቢው አጣሪ ቡድን ልኮ የሶማሌላንድ ጥያቄ በቅኝ ግዛት ድንበር እና በቀድሞ ነጻነቷ ላይ የተመሰረተ ታሪካዊ መነሻ እንዳለው ቢገነዘብም፣ አሁንም ድረስ ለሶማሊያ ሉዓላዊነት እና የግዛት አንድነት ቅድሚያ መስጠትን መርጧል። በርካታ የአፍሪካ ሀገራት ሶማሌላንድን እውቅና መስጠት በሌሎች አካባቢዎች የመገንጠል ጥያቄዎችን ሊያነሳሳ ይችላል የሚል ስጋት አላቸው። ሶማሌላንድ በበኩሏ የድሮውን ድንበር መመለስ እንጂ አዲስ ድንበር መፍጠር አይደለም ስትል ምላሽ ትሰጣለች።
ሶማሌላንድ በቅኝ ግዛት ድንበር እና በቀድሞ ነጻነት ላይ የተመሰረተ ጠንካራ የህግ መከራከሪያ ብታቀርብም፣ የኤርትራን ተሞክሮ ስንመለከት የህግ ትንታኔ ብቻውን እውቅናን እንደማያመጣ መገንዘብ ይቻላል። ሶማሌላንድ ከሶማሊያ ጋር የደረሰችበት ምንም አይነት ስምምነት ባለመኖሩ፣ የእውቅና ጉዳይ አሁንም ድረስ አለም አቀፍ ተቋማት የድሮዋን ሉዓላዊ ሀገር ዳግም መመለስ አድርገው ይቀበሉታል ወይስ የሶማሊያን የግዛት አንድነት የሚፈታተን ድርጊት አድርገው ይቆጥሩታል የሚለው ጉዳይ የፈተና መድረክ ሆኖ ቀጥሏል።
የሶማሌላንድ ዋነኛ የህግ መከራከሪያ አዲስ ነጻ የሚወጡ ሀገራት በቅኝ ግዛት ወቅት የነበራቸውን ድንበር ጠብቀው ሊቀጥሉ ይገባል የሚለው መርህ ነው። የአፍሪካ አንድነት ድርጅት በ1964ቱ የካይሮ ውሳኔው እንዲሁም የአፍሪካ ህብረት የመመስረቻ ሰነዱ ላይ አባል ሀገራት በነጻነት ጊዜ የነበራቸውን ድንበር ሊያከብሩ እንደሚገባ አስፍረዋል። በመሆኑም ሶማሌላንድ አለም አቀፍ እውቅና ማግኘቷ የቅኝ ግዛት ድንበርን ከመጠበቅ ባለፈ አዲስ ድንበር የማካለል ስራ አይደለም በማለት ትከራከራለች። አቋሟም ከዚህ ቀደም ሉዓላዊ ሀገር እንደነበረች፣ የ1960ውን ውህደት በራሷ ፈቃድ እንደፈጸመች እና የ1991ዱ እርምጃዋም የከሸፈን ውህደት ማፍረስ እንጂ አዲስ ግዛትን ከሶማሊያ መገንጠል አይደለም በሚሉ ሶስት ምሶሶዎች ላይ የቆመ ነው። ይህ አቀራረብ ሶማሌላንድን ምንም አይነት የቅኝ ግዛት ወይም አለም አቀፍ ድንበር መሰረት ከሌላቸው የመገንጠል ጥያቄዎች የተለየች ያደርጋታል።
የሶማሌላንድን ሁኔታ ከኤርትራ ጋር ማነጻጸር የጉዳዩን የዲፕሎማሲ ውስብስብነት በደንብ ያሳያል። ሁለቱም ግዛቶች የተለየ የቅኝ ግዛት ታሪክ፣ ከማዕከላዊ መንግስት ጋር የተደረገ የትጥቅ ትግል እና ከ1991 በኋላ ውጤታማ የሆነ ራስን በራስ የማስተዳደር ልምድ አላቸው። ይሁን እንጂ የኤርትራ የነጻነት ጥያቄ የኢትዮጵያን የሽግግር መንግስት ፈቃድ እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የህዝበ ውሳኔ ታዛቢነትን በማግኘቱ ፈጣን አለም አቀፍ እውቅናን ሊያጎናጽፋት ችሏል። በሶማሌላንድ በኩል ግን ጠንካራ ተቋማትን መገንባት እና ህዝበ ውሳኔ ማካሄድ ብትችልም፣ ከሶማሊያ መንግስት የተገኘ ስምምነትም ሆነ እንደ ኤርትራው አይነት አለም አቀፍ ድጋፍ ባለማግኘቷ የዲፕሎማሲ እውቅናው ሊዘገይባት ችሏል። ይህ የሚያሳየው ውጤታማ አስተዳደር እና ታሪካዊ ድንበር መኖር ብቻውን በቂ እንዳልሆነ እና እውቅና ማግኘት በስምምነት፣ በቀጠናዊ ፖለቲካ እና በዲፕሎማሲያዊ ድጋፍ ላይ በእጅጉ የተመሰረተ መሆኑን ነው።
የአፍሪካ ህብረት በ2005 ወደ አካባቢው አጣሪ ቡድን ልኮ የሶማሌላንድ ጥያቄ በቅኝ ግዛት ድንበር እና በቀድሞ ነጻነቷ ላይ የተመሰረተ ታሪካዊ መነሻ እንዳለው ቢገነዘብም፣ አሁንም ድረስ ለሶማሊያ ሉዓላዊነት እና የግዛት አንድነት ቅድሚያ መስጠትን መርጧል። በርካታ የአፍሪካ ሀገራት ሶማሌላንድን እውቅና መስጠት በሌሎች አካባቢዎች የመገንጠል ጥያቄዎችን ሊያነሳሳ ይችላል የሚል ስጋት አላቸው። ሶማሌላንድ በበኩሏ የድሮውን ድንበር መመለስ እንጂ አዲስ ድንበር መፍጠር አይደለም ስትል ምላሽ ትሰጣለች።
ሶማሌላንድ በቅኝ ግዛት ድንበር እና በቀድሞ ነጻነት ላይ የተመሰረተ ጠንካራ የህግ መከራከሪያ ብታቀርብም፣ የኤርትራን ተሞክሮ ስንመለከት የህግ ትንታኔ ብቻውን እውቅናን እንደማያመጣ መገንዘብ ይቻላል። ሶማሌላንድ ከሶማሊያ ጋር የደረሰችበት ምንም አይነት ስምምነት ባለመኖሩ፣ የእውቅና ጉዳይ አሁንም ድረስ አለም አቀፍ ተቋማት የድሮዋን ሉዓላዊ ሀገር ዳግም መመለስ አድርገው ይቀበሉታል ወይስ የሶማሊያን የግዛት አንድነት የሚፈታተን ድርጊት አድርገው ይቆጥሩታል የሚለው ጉዳይ የፈተና መድረክ ሆኖ ቀጥሏል።
5 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) በሽራሮ አቅራቢያ ዳግም ውጊያ ማገርሸቱን ተከትሎ፣ በፌደራል መንግስቱ እና በትግራይ ኃይሎች መካከል የተደረገውን የሶስት ዓመት የሰላም ስምምነት ክፉኛ የጣሰ ከባድ ክስተት ተፈጥሯል።
በመቀሌ የሚገኘው የትግራይ ክልላዊ መንግስት ባወጣው መግለጫ፣ የፌደራል መንግስት ኃይሎች ቅዳሜ ንጋት ላይ ከሱዳን ድንበር አቅራቢያ ከሸራሮ አቅጣጫ ጥቃት መክፈታቸውን አስታውቋል። በጦርነቱ ወቅት የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደርን የመሩት ሚኒስትሩ ዶክተር አብርሃም በላይ በበኩላቸው፣ ግጭት መፈጠሩን አረጋግጠው፤ ነገር ግን ጥቃቱን የጀመሩት በህወሓት ሊቀመንበር ዶክተር ደብረፅዮን ገብረሚካኤል የሚመሩ ኃይሎች መሆናቸውን በመግለጽ ከሰዋል። ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው "ጦርነት ይብቃ! ልዩነቶቻችንን በውይይት እንፍታ" ሲሉ አሳስበዋል።
ይህ ግጭት የተከሰተው ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ እ.ኤ.አ. በ2018 ወደ ስልጣን ከመምጣታቸው በፊት ለሶስት አስርት ዓመታት ኢትዮጵያን ያስተዳደረው ህወሓት እና አዲስ አበባ ላለፉት ወራት እያሽቆለቆለ የመጣውን ግንኙነት ተከትሎ ነው። ሁለቱም ወገኖች የ2022ቱን (የ2015 ዓ.ም) የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት ድንጋጌዎችን ተግባራዊ አላደረጉም በሚል እርስ በእርስ ሲወነጃጀሉ ቆይተዋል።
የትግራይ ባለስልጣናት ገዢው ብልጽግና ፓርቲ በክልሉ ላይ የረጅም ጊዜ እገዳ እና የድሮን ጥቃት ዘመቻ ሲያካሂድ መቆየቱን እና ይህ አሁን ወደ ሙሉ ጦርነት ማደጉን ገልጸዋል። የክልሉ መንግስት የትግራይ ኃይሎች፣ የሲቪል ማህበረሰብ እና የሀይማኖት ተቋማት "ለሀገር ጥፋት እምቢ" በሚል መሪ ቃል ለብሔራዊ ህልውና ትግል እንዲዘጋጁ ጥሪ አቅርቧል።
በሌላ በኩል የቀድሞው የህወሓት ቃል አቀባይ እና የአሁኑ የጠቅላይ ሚኒስትሩ አማካሪ አቶ ጌታቸው ረዳ፣ ዶክተር ደብረፅዮን በኤርትራ እና በአማራ ታጣቂዎች ላይ ተማምነው በጉልበት ወደ ስልጣን ለመመለስ እየሞከሩ ነው ሲሉ በመክሰስ የትግራይ ሰራዊት አመራሮች እርሳቸውን (ደብረፅዮንን) እንዲተዉ አሳስበዋል። እ.ኤ.አ. በ2022 ለህወሓት እና ለፌደራል መንግስቱ የፕሪቶሪያውን ስምምነት የፈረሙት አቶ ጌታቸው እና የደህንነት ሹሙ አቶ ሬድዋን ሁሴን፣ ባለፈው ሰኔ ወር በአልጀዚራ ላይ በጋራ ባወጡት ጽሁፍ ጦርነት ሊቀሰቀስ እንደሚችል ማስጠንቀቃቸው ይታወሳል።
በኦስሎ ኒው ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ የኢትዮጵያ ጉዳዮች ተንታኝ የሆኑት ቸቲል ትሮንቮል ለአልጀዚራ እንደተናገሩት፣ ይህ ውጊያ ከ2022ቱ የሰላም ስምምነት ወዲህ የታየ "እጅግ አሳሳቢው ክስተት" ነው። ስምምነቱ ጦርነቱን ቢያስቆምም፣ በመቀሌ እና አዲስ አበባ መካከል ያለውን "የግጭቱን መሰረታዊ ምክንያቶች" ሳይፈታ ማለፉን አክለዋል። ለዚህ ግጭት መነሻ በሆኑት ቀናት ውስጥ፣ የኢትዮጵያ መንግስት መገናኛ ብዙሃን ዶክተር ደብረፅዮንን በስማቸው ጠቅሰው ትግራውያንን ለጦርነት እየቀሰቀሱ ነው የሚል የክስ ዘመቻ ሲያካሂዱ ነበር።
ከሁለት ዓመታት በፊት ተጀምሮ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎችን ህይወት የቀጠፈውን ጦርነት ያስቆመው የፕሪቶሪያው ስምምነት፣ የትጥቅ አፈታት እና የህወሓትን ህጋዊ ሰውነት በተመለከቱ ጥልቅ ጉዳዮች ላይ እልባት ሳይሰጥ ቆይቷል። ይህንም ተከትሎ አሜሪካ ባለፈው ሰኔ ወር ሰላምን ያደናቅፋሉ ባላቸው የህወሓት "አክራሪዎች" ላይ የቪዛ ማዕቀብ የጣለች ሲሆን፣ ህወሓትም እርምጃው ያልተሟላ እና ሚዛናዊ ያልሆነ መረጃ ላይ የተመሰረተ ነው ሲል ተችቶታል።
የዩናይትድ ስቴትስ አምባሳደር ኤርቪን ማሲንጋ ስምምነቱን ለማትረፍ ወደ መቀሌ ቢያቀኑም፣ በሀምሌ ወር አጋማሽ ህወሓት የፕሪቶሪያው ስምምነት "በተግባር ሞቷል" ሲል አውጇል። የቀጠናው ተንታኝ ፋይሰል ሮብሌ ይህ የውጊያ ጅማሮ አሜሪካ በሁለቱ ወገኖች መካከል ያለውን አለመግባባት ለመፍታት ያደረገችው ጥረት አለመሳካቱን የሚያሳይ ነው ብለዋል። አክለውም "ጠንካራ ዓለም አቀፍ ጣልቃ ገብነት ከሌለ፣ ወደ እጅግ የሰፋ ጦርነት ልናመራ እንችላለን" ሲሉ አስጠንቅቀዋል።
በመቀሌ የሚገኘው የትግራይ ክልላዊ መንግስት ባወጣው መግለጫ፣ የፌደራል መንግስት ኃይሎች ቅዳሜ ንጋት ላይ ከሱዳን ድንበር አቅራቢያ ከሸራሮ አቅጣጫ ጥቃት መክፈታቸውን አስታውቋል። በጦርነቱ ወቅት የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደርን የመሩት ሚኒስትሩ ዶክተር አብርሃም በላይ በበኩላቸው፣ ግጭት መፈጠሩን አረጋግጠው፤ ነገር ግን ጥቃቱን የጀመሩት በህወሓት ሊቀመንበር ዶክተር ደብረፅዮን ገብረሚካኤል የሚመሩ ኃይሎች መሆናቸውን በመግለጽ ከሰዋል። ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው "ጦርነት ይብቃ! ልዩነቶቻችንን በውይይት እንፍታ" ሲሉ አሳስበዋል።
ይህ ግጭት የተከሰተው ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ እ.ኤ.አ. በ2018 ወደ ስልጣን ከመምጣታቸው በፊት ለሶስት አስርት ዓመታት ኢትዮጵያን ያስተዳደረው ህወሓት እና አዲስ አበባ ላለፉት ወራት እያሽቆለቆለ የመጣውን ግንኙነት ተከትሎ ነው። ሁለቱም ወገኖች የ2022ቱን (የ2015 ዓ.ም) የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት ድንጋጌዎችን ተግባራዊ አላደረጉም በሚል እርስ በእርስ ሲወነጃጀሉ ቆይተዋል።
የትግራይ ባለስልጣናት ገዢው ብልጽግና ፓርቲ በክልሉ ላይ የረጅም ጊዜ እገዳ እና የድሮን ጥቃት ዘመቻ ሲያካሂድ መቆየቱን እና ይህ አሁን ወደ ሙሉ ጦርነት ማደጉን ገልጸዋል። የክልሉ መንግስት የትግራይ ኃይሎች፣ የሲቪል ማህበረሰብ እና የሀይማኖት ተቋማት "ለሀገር ጥፋት እምቢ" በሚል መሪ ቃል ለብሔራዊ ህልውና ትግል እንዲዘጋጁ ጥሪ አቅርቧል።
በሌላ በኩል የቀድሞው የህወሓት ቃል አቀባይ እና የአሁኑ የጠቅላይ ሚኒስትሩ አማካሪ አቶ ጌታቸው ረዳ፣ ዶክተር ደብረፅዮን በኤርትራ እና በአማራ ታጣቂዎች ላይ ተማምነው በጉልበት ወደ ስልጣን ለመመለስ እየሞከሩ ነው ሲሉ በመክሰስ የትግራይ ሰራዊት አመራሮች እርሳቸውን (ደብረፅዮንን) እንዲተዉ አሳስበዋል። እ.ኤ.አ. በ2022 ለህወሓት እና ለፌደራል መንግስቱ የፕሪቶሪያውን ስምምነት የፈረሙት አቶ ጌታቸው እና የደህንነት ሹሙ አቶ ሬድዋን ሁሴን፣ ባለፈው ሰኔ ወር በአልጀዚራ ላይ በጋራ ባወጡት ጽሁፍ ጦርነት ሊቀሰቀስ እንደሚችል ማስጠንቀቃቸው ይታወሳል።
በኦስሎ ኒው ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ የኢትዮጵያ ጉዳዮች ተንታኝ የሆኑት ቸቲል ትሮንቮል ለአልጀዚራ እንደተናገሩት፣ ይህ ውጊያ ከ2022ቱ የሰላም ስምምነት ወዲህ የታየ "እጅግ አሳሳቢው ክስተት" ነው። ስምምነቱ ጦርነቱን ቢያስቆምም፣ በመቀሌ እና አዲስ አበባ መካከል ያለውን "የግጭቱን መሰረታዊ ምክንያቶች" ሳይፈታ ማለፉን አክለዋል። ለዚህ ግጭት መነሻ በሆኑት ቀናት ውስጥ፣ የኢትዮጵያ መንግስት መገናኛ ብዙሃን ዶክተር ደብረፅዮንን በስማቸው ጠቅሰው ትግራውያንን ለጦርነት እየቀሰቀሱ ነው የሚል የክስ ዘመቻ ሲያካሂዱ ነበር።
ከሁለት ዓመታት በፊት ተጀምሮ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎችን ህይወት የቀጠፈውን ጦርነት ያስቆመው የፕሪቶሪያው ስምምነት፣ የትጥቅ አፈታት እና የህወሓትን ህጋዊ ሰውነት በተመለከቱ ጥልቅ ጉዳዮች ላይ እልባት ሳይሰጥ ቆይቷል። ይህንም ተከትሎ አሜሪካ ባለፈው ሰኔ ወር ሰላምን ያደናቅፋሉ ባላቸው የህወሓት "አክራሪዎች" ላይ የቪዛ ማዕቀብ የጣለች ሲሆን፣ ህወሓትም እርምጃው ያልተሟላ እና ሚዛናዊ ያልሆነ መረጃ ላይ የተመሰረተ ነው ሲል ተችቶታል።
የዩናይትድ ስቴትስ አምባሳደር ኤርቪን ማሲንጋ ስምምነቱን ለማትረፍ ወደ መቀሌ ቢያቀኑም፣ በሀምሌ ወር አጋማሽ ህወሓት የፕሪቶሪያው ስምምነት "በተግባር ሞቷል" ሲል አውጇል። የቀጠናው ተንታኝ ፋይሰል ሮብሌ ይህ የውጊያ ጅማሮ አሜሪካ በሁለቱ ወገኖች መካከል ያለውን አለመግባባት ለመፍታት ያደረገችው ጥረት አለመሳካቱን የሚያሳይ ነው ብለዋል። አክለውም "ጠንካራ ዓለም አቀፍ ጣልቃ ገብነት ከሌለ፣ ወደ እጅግ የሰፋ ጦርነት ልናመራ እንችላለን" ሲሉ አስጠንቅቀዋል።
Sponsored by
Surafel
5 days ago
"ኮከል ማሚቶ" : በካፋ ባህል ላይ የሚያተኩር የኢትኖግራፊ መጽሐፍ በቦንጋ ነገ ይመረቃል
#ethiopia | በካፋ ባህል፣ ታሪክ እና የማህበረሰቡ የኑሮ ዘይቤ ላይ የሚያተኩረው "ኮከል ማሚቶ" የተሰኘ የኢትኖግራፊ መጽሐፍ እሁድ፣ ሐምሌ 26 / 2018ዓ.ም ከቀኑ 8:00 ሰዓት በቦንጋ ከተማ በICT አዳራሽ በይፋ ይመረቃል።
መጽሐፉ በአምስት ዋና ዋና ክፍሎች የተደራጀ ሲሆን፣ የካፋን ማህበረሰብ ከሙዚቃ፣ ከመናፍስት እምነቶች፣ ከጦረኝነት ባህል፣ ከተፈጥሮ ጋር ካለው ትስስር እንዲሁም ከአዕዋፋት ጋር የተያያዙ በርካታ ባህላዊና ማህበራዊ ጉዳዮችን በሰፊው ይዳስሳል።
በባህል፣ በማህበረሰብ እና በነባር የኑሮ ትስስር ላይ የሚያተኩሩ የኢትኖግራፊ ሥራዎች በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ እምብዛም በማይገኙበት ሁኔታ፣ "ኮከል ማሚቶ" በዘርፉ አዲስ አቅጣጫ የሚከፍት እና ለቀጣይ የምርምርና የጽሑፍ ሥራዎች መነሻ የሚሆን መጽሐፍ እንደሚሆን ተስፋ ተጥሎበታል።
የመጽሐፉ ምረቃ ሥነ ሥርዓት የባህል ባለሙያዎችን፣ የሥነ ጽሑፍ ወዳጆችን፣ ተመራማሪዎችን እና የካፋ ባህልን ለማወቅ ፍላጎት ያላቸውን ሁሉ እንዲታደሙ ጥሪ ያቀርባል።
#ethiopia | በካፋ ባህል፣ ታሪክ እና የማህበረሰቡ የኑሮ ዘይቤ ላይ የሚያተኩረው "ኮከል ማሚቶ" የተሰኘ የኢትኖግራፊ መጽሐፍ እሁድ፣ ሐምሌ 26 / 2018ዓ.ም ከቀኑ 8:00 ሰዓት በቦንጋ ከተማ በICT አዳራሽ በይፋ ይመረቃል።
መጽሐፉ በአምስት ዋና ዋና ክፍሎች የተደራጀ ሲሆን፣ የካፋን ማህበረሰብ ከሙዚቃ፣ ከመናፍስት እምነቶች፣ ከጦረኝነት ባህል፣ ከተፈጥሮ ጋር ካለው ትስስር እንዲሁም ከአዕዋፋት ጋር የተያያዙ በርካታ ባህላዊና ማህበራዊ ጉዳዮችን በሰፊው ይዳስሳል።
በባህል፣ በማህበረሰብ እና በነባር የኑሮ ትስስር ላይ የሚያተኩሩ የኢትኖግራፊ ሥራዎች በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ እምብዛም በማይገኙበት ሁኔታ፣ "ኮከል ማሚቶ" በዘርፉ አዲስ አቅጣጫ የሚከፍት እና ለቀጣይ የምርምርና የጽሑፍ ሥራዎች መነሻ የሚሆን መጽሐፍ እንደሚሆን ተስፋ ተጥሎበታል።
የመጽሐፉ ምረቃ ሥነ ሥርዓት የባህል ባለሙያዎችን፣ የሥነ ጽሑፍ ወዳጆችን፣ ተመራማሪዎችን እና የካፋ ባህልን ለማወቅ ፍላጎት ያላቸውን ሁሉ እንዲታደሙ ጥሪ ያቀርባል።
5 days ago
ስደተኞቹ ሳይገቡ ወጥተዋል
#ethiopia | በትላንትናው እለት ከሞሮኮ መነሻቸውን አድርገው ስፔንን አጥለቅልቀው የነበሩት ስደተኞች ወደ መጡበት እየተመለሱ ይገኛል።
ኪዩታ ወደ ተሰኘችው የስፔን ከተማ የገቡት 60,000 የሚጠጉ ስደተኞቹ በዛሬው እለት ወደ ሞሮኮ በፍቃደኝነት እየተመለሱ መሆናቸውን አልጀዚራ ጽፏል።
የስፔን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጆዜ ማኑኤል አልቫሬዝ እንደገለፁት ሀገራቸው የስደተኞች ነፃነትና መብት እንደምታከብር ገልጸው ህገወጥ መንገድ ግን በየትኛውም መንገድ አንቀበልም ብለዋል።
አሁን በወጡ መረጃዎች መሠረት በህገወጥ መንገድ ከገቡት ስደተኞች መካከል 67 የሚሆኑት ህይወታቸው አልፏል ሲሉም ተናግረዋል።
የአውሮፓ ህብረት ሀላፊ ኡርሱላ ቮንደርላይን የስደተኞቹ ድርጊት ተቀባይነት እንደሌለው ተናግረው ሀገራት ድንበራቸውን ጥብቅ እንዲያደርጉ አሳስበዋል።
የፈረንሳይ የሀገር ውስጥ ሚኒስትር በበኩላቸው ሀገራቸውን ከስፔን የምትዋሰንበት ድንበር ማጠናከሯን ገልጸዋል።
የስፔኑ ጠቅላይ ሚኒስትር ፔድሮ ሳንቼዝ ድንበሮቻቸውን ክፍት አድርገው ስፔንን በስደተኞች እንድትወረር ያደረጉ ሀገራትን ክፍኛ ተችተዋል።
ሔኖክ ወ/ገብርኤል
#ethiopia #getutemesgen #getunews #spain #migrants #ceuta #europeanunion #ursulavonderleyen
#ethiopia | በትላንትናው እለት ከሞሮኮ መነሻቸውን አድርገው ስፔንን አጥለቅልቀው የነበሩት ስደተኞች ወደ መጡበት እየተመለሱ ይገኛል።
ኪዩታ ወደ ተሰኘችው የስፔን ከተማ የገቡት 60,000 የሚጠጉ ስደተኞቹ በዛሬው እለት ወደ ሞሮኮ በፍቃደኝነት እየተመለሱ መሆናቸውን አልጀዚራ ጽፏል።
የስፔን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጆዜ ማኑኤል አልቫሬዝ እንደገለፁት ሀገራቸው የስደተኞች ነፃነትና መብት እንደምታከብር ገልጸው ህገወጥ መንገድ ግን በየትኛውም መንገድ አንቀበልም ብለዋል።
አሁን በወጡ መረጃዎች መሠረት በህገወጥ መንገድ ከገቡት ስደተኞች መካከል 67 የሚሆኑት ህይወታቸው አልፏል ሲሉም ተናግረዋል።
የአውሮፓ ህብረት ሀላፊ ኡርሱላ ቮንደርላይን የስደተኞቹ ድርጊት ተቀባይነት እንደሌለው ተናግረው ሀገራት ድንበራቸውን ጥብቅ እንዲያደርጉ አሳስበዋል።
የፈረንሳይ የሀገር ውስጥ ሚኒስትር በበኩላቸው ሀገራቸውን ከስፔን የምትዋሰንበት ድንበር ማጠናከሯን ገልጸዋል።
የስፔኑ ጠቅላይ ሚኒስትር ፔድሮ ሳንቼዝ ድንበሮቻቸውን ክፍት አድርገው ስፔንን በስደተኞች እንድትወረር ያደረጉ ሀገራትን ክፍኛ ተችተዋል።
ሔኖክ ወ/ገብርኤል
#ethiopia #getutemesgen #getunews #spain #migrants #ceuta #europeanunion #ursulavonderleyen
6 days ago
የጥቃቱ መነሻ‼️
👉 የጥቃቱ መነሻና ቦታ፡ አካባቢውን በኃይል ለመቆጣጠር በማሰብ፣ በሱዳን በኩል የተደራጁ የ'ሳምሪ' ታጣቂ ኃይሎች ዛሬ ጠዋት በኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ላይ ወታደራዊ ጥቃት ከፍተዋል። ታጣቂዎቹ ጦርነቱን የጀመሩት በሱዳን ድንበር በኩል በ'ሸረሪና' እና በወልቃይት ጠገዴ ዞን፣ ቃብትያ ሁመራ ወረዳ ስር በምትተዳደረው የበረከት ከተማ አቅጣጫ ድንበር ጥሰው በመግባት ነው።
👉 የሜዳ ላይ ውጊያ ሁኔታ፡ በበረከት ከተማ እና በሸረሪና አቅጣጫ ጥቃቱን የጀመሩት ከሱዳን ሰርጎ የገቡት ታጣቂዎች ('አርሚ 70' ላይ) በቀላል መሳሪያዎች ትንኮሳ የከፈቱ ሲሆን፣ ይህንን ተከትሎ የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት መጠነ ሰፊ የአፀፋ እርምጃ መውሰድ ጀምሯል።
👉 በድሮንና በመድፍ የታገዘ አፀፋ፡ አሁን ላይ ከሁመራ ወደ በረከት ከተማ እና ሸረሪና አቅጣጫ ከፍተኛ የሆነ የመድፍ ድብደባ እየተካሄደ ሲሆን፣ በሰማይ ላይም የድሮን እንቅስቃሴ በግልፅ እየታየ ነው። የከባድ መሳሪያው (መድፍ) ተኩስ እጅግ ከፍተኛ ከመሆኑ የተነሳ ርቀት ላይ በምትገኘው ሁመራ ከተማ ውስጥ ያሉ መኖሪያ ቤቶችን በከፍተኛ ሁኔታ እያነዘረ እንደሚገኝ ነዋሪዎች አረጋግጠዋል።
👉 የመከላከያ ሠራዊት እርምጃ፡ በበረከት እና ሸረሪና አቅጣጫ የተጀመረውን የተኩስ ልውውጥ ተከትሎ በአካባቢው ከፍተኛ ወታደራዊ ውጥረት ያንዣበበ ሲሆን፤ የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት የተከፈተበትን ይህንን ጥቃት ሙሉ በሙሉ ለመመከት እና ለመደምሰስ በከፍተኛ ዝግጅት ላይ መሆኑን ከስፍራው የወጡ መረጃዎች አረጋግጠዋል።
👉በድምፅ አልባ መሳሪያ (መሬት ላይ ሲደርስ ብቻ የሚፈነዳ መሳሪያ) በርካታ የአርሚ 70 ታጣቂዎች ላይ ጉዳት ማድረሱን ምንጮች ጠቁመዋል።
👉ታጣቂዎቹ ዛሬ ሁመራን ለመያዝ እቅድ እንደሰጣቸው ገልፀዋል።
👉ህወሓት በበኩሉ የፌደራል መንግስቱ ከበባ ሲፈፅም ከርሞ ዛሬ ሐምሌ 25/2018 ዓ.ም በምዕራብ ትግራይ ተኩስ ከፍቶብናል ሲል መግለጫ አውጥቷል።
Seledadotio
Seledadotio
👉 የጥቃቱ መነሻና ቦታ፡ አካባቢውን በኃይል ለመቆጣጠር በማሰብ፣ በሱዳን በኩል የተደራጁ የ'ሳምሪ' ታጣቂ ኃይሎች ዛሬ ጠዋት በኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ላይ ወታደራዊ ጥቃት ከፍተዋል። ታጣቂዎቹ ጦርነቱን የጀመሩት በሱዳን ድንበር በኩል በ'ሸረሪና' እና በወልቃይት ጠገዴ ዞን፣ ቃብትያ ሁመራ ወረዳ ስር በምትተዳደረው የበረከት ከተማ አቅጣጫ ድንበር ጥሰው በመግባት ነው።
👉 የሜዳ ላይ ውጊያ ሁኔታ፡ በበረከት ከተማ እና በሸረሪና አቅጣጫ ጥቃቱን የጀመሩት ከሱዳን ሰርጎ የገቡት ታጣቂዎች ('አርሚ 70' ላይ) በቀላል መሳሪያዎች ትንኮሳ የከፈቱ ሲሆን፣ ይህንን ተከትሎ የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት መጠነ ሰፊ የአፀፋ እርምጃ መውሰድ ጀምሯል።
👉 በድሮንና በመድፍ የታገዘ አፀፋ፡ አሁን ላይ ከሁመራ ወደ በረከት ከተማ እና ሸረሪና አቅጣጫ ከፍተኛ የሆነ የመድፍ ድብደባ እየተካሄደ ሲሆን፣ በሰማይ ላይም የድሮን እንቅስቃሴ በግልፅ እየታየ ነው። የከባድ መሳሪያው (መድፍ) ተኩስ እጅግ ከፍተኛ ከመሆኑ የተነሳ ርቀት ላይ በምትገኘው ሁመራ ከተማ ውስጥ ያሉ መኖሪያ ቤቶችን በከፍተኛ ሁኔታ እያነዘረ እንደሚገኝ ነዋሪዎች አረጋግጠዋል።
👉 የመከላከያ ሠራዊት እርምጃ፡ በበረከት እና ሸረሪና አቅጣጫ የተጀመረውን የተኩስ ልውውጥ ተከትሎ በአካባቢው ከፍተኛ ወታደራዊ ውጥረት ያንዣበበ ሲሆን፤ የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት የተከፈተበትን ይህንን ጥቃት ሙሉ በሙሉ ለመመከት እና ለመደምሰስ በከፍተኛ ዝግጅት ላይ መሆኑን ከስፍራው የወጡ መረጃዎች አረጋግጠዋል።
👉በድምፅ አልባ መሳሪያ (መሬት ላይ ሲደርስ ብቻ የሚፈነዳ መሳሪያ) በርካታ የአርሚ 70 ታጣቂዎች ላይ ጉዳት ማድረሱን ምንጮች ጠቁመዋል።
👉ታጣቂዎቹ ዛሬ ሁመራን ለመያዝ እቅድ እንደሰጣቸው ገልፀዋል።
👉ህወሓት በበኩሉ የፌደራል መንግስቱ ከበባ ሲፈፅም ከርሞ ዛሬ ሐምሌ 25/2018 ዓ.ም በምዕራብ ትግራይ ተኩስ ከፍቶብናል ሲል መግለጫ አውጥቷል።
Seledadotio
Seledadotio
6 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) "የሰኔ 15ቱ ክስተት መነሻ አድርጌ የምወስደው ቤዚክሊ ሁለት፣ ከሁለት ጉዳዮች የሆነ ይመስለኛል። አንደኛው ስሁት ግምገማ ነው፤ አንድ ነገር ለማሳካት የምትሰራው ግምገማ በበቂ ዳታ ላይ፣ በበቂ ኢንፎርሜሽን ላይ ያልተመሰረተ ከሆነ፣ ጉጉት ይቀድምና መሻት ይፈጥርና ወደዚያ ለማድረስ የሚገባህን መንገድ በትክክል ዲዛይን ሳታደርግ ጥፋት ታመጣለህና ስሁት ግምገማ አንዱ ችግር ይመስለኛል። ይሄ እዛ ላይ ያበቃ ሳይሆን ከዛ በኋላም በተደጋጋሚ የምናየው ችግር ነው።
"ሁለተኛው ችግር በሁለት እግር ማነከስ ነው። ለውጥ ተቀብለህ፣ ሀላፊነት ተቀብለህ፣ የህዝብ አደራ ተቀብለህ በሌላ መንገድ ደግሞ ያልተቀደሰ ጋብቻ ከመደበኛ ሀይሎች ጋር አድርገህ እዚሁም እዚያም ለመሆን የሚፈለግ ሁኔታ በአንዳንድ ሰዎች ይታይ ነበረ፤ ያም የፈጠረው ይመስለኛል። ግምገማውም ችግር አለ፣ እንደገና ደግሞ በሁለት እግር ማነከሱም አለ፣ እዚህ ተቀምጦ እዚያ፣ እዚያ ሆኖ ደግሞ እዚህ የመሻቱ ፍላጎት የተቀላቀሉ ነገሮች አሉ። በአንድ መንግስት ወይም በአንድ ፓርቲ እቅድ የሚመራ ስብስብ ሳይሆን፣ እቅዱን ከተለያየ ሶርስ የሚወስድ ሀይል ያለበት፣ ግን በጋራ የሚነጋገር የሚሰበሰብ የሚወያይ፣ በዛ ሂደት ደግሞ ጥፋት ሊያመጣ የሚችል ክስተት ሆኗል።
"እንግዲህ ቅድም ላነሳልህ እንደሞከርኩት የኢትዮጵያ ህዝቦች የመዋሀድ ታሪክ ቢኖራቸውም፣ አብሮ የመዝመት ታሪክ ቢኖራቸውም፣ በዘመናት መካከል ስልጣን ሲመጣ በሀይል፣ አልጋ ሳይጸና የመገዳደል ፍላጎት የባህላችን አንዱ አካል ነው። ልጅ ኢያሱ ዘመን መለስ ብለህ ወደ ታሪክ ብታገላብጥ ይሄን ነገር በቀላሉ ማየት ትችላለህ። በዘመነ መሳፍንት የምንለውን፣ በኋላ 1966 ላይ ያጋጠመውን ብንወስድ የዚሁ ተቀጽላ ነው፣ በደርግ ዘመን 1981 ያየነው መሰል ባህሪ ነው፣ በኢህአዴግ ዘመን መጠኑ ዝቅ ያለ ቢሆንም በ2001 አካባቢ መጠነኛ ፍላጎቶች ተንጸባርቀዋል። በእኛም ጊዜ በሰኔ 2010 16 ላይ ከለውጡ ሁለት ወር ሶስት ወር በኋላ መሰል ሙከራዎች በመስቀል አደባባይ ተካሂደዋል። እዚህ በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ ሁልጊዜም በሀይል ፍላጎትን ማሳካት፣ በሀይል ስልጣን ለመያዝ መሞከር፣ ሰው በመግደል ስልጣን ለመውረስ መሞከር ነበረ ማለት ነው።
"የሰኔ 15ቱም ከነዚህ ከላይ ከዘረዘርኳቸው ክስተቶች ለየት የሚያደርገው በክልል ደረጃ፣ በከተማ ደረጃ ዝቅ ብሎ ለመፈጸም የተሞከረ ሙከራ ነው። በክልል ደረጃ እንደዚህ ያለውን ጉዳይ ፈጽመህ ምን ታሳካለህ የሚለው ጉዳይ ቅድም ያልኩት የስሁት ግምገማ ውጤት አካል ይመስለኛል። እንዴት ታስታውሰዋለህ እንዴት ይታወሳል አልከው፣ የታሪካችን የጠባሳችን አካል አድርጌ ነው ማስታውሰው።"
- ጠቅላይ ሚ/ር ዐቢይ አህመድ
"ሁለተኛው ችግር በሁለት እግር ማነከስ ነው። ለውጥ ተቀብለህ፣ ሀላፊነት ተቀብለህ፣ የህዝብ አደራ ተቀብለህ በሌላ መንገድ ደግሞ ያልተቀደሰ ጋብቻ ከመደበኛ ሀይሎች ጋር አድርገህ እዚሁም እዚያም ለመሆን የሚፈለግ ሁኔታ በአንዳንድ ሰዎች ይታይ ነበረ፤ ያም የፈጠረው ይመስለኛል። ግምገማውም ችግር አለ፣ እንደገና ደግሞ በሁለት እግር ማነከሱም አለ፣ እዚህ ተቀምጦ እዚያ፣ እዚያ ሆኖ ደግሞ እዚህ የመሻቱ ፍላጎት የተቀላቀሉ ነገሮች አሉ። በአንድ መንግስት ወይም በአንድ ፓርቲ እቅድ የሚመራ ስብስብ ሳይሆን፣ እቅዱን ከተለያየ ሶርስ የሚወስድ ሀይል ያለበት፣ ግን በጋራ የሚነጋገር የሚሰበሰብ የሚወያይ፣ በዛ ሂደት ደግሞ ጥፋት ሊያመጣ የሚችል ክስተት ሆኗል።
"እንግዲህ ቅድም ላነሳልህ እንደሞከርኩት የኢትዮጵያ ህዝቦች የመዋሀድ ታሪክ ቢኖራቸውም፣ አብሮ የመዝመት ታሪክ ቢኖራቸውም፣ በዘመናት መካከል ስልጣን ሲመጣ በሀይል፣ አልጋ ሳይጸና የመገዳደል ፍላጎት የባህላችን አንዱ አካል ነው። ልጅ ኢያሱ ዘመን መለስ ብለህ ወደ ታሪክ ብታገላብጥ ይሄን ነገር በቀላሉ ማየት ትችላለህ። በዘመነ መሳፍንት የምንለውን፣ በኋላ 1966 ላይ ያጋጠመውን ብንወስድ የዚሁ ተቀጽላ ነው፣ በደርግ ዘመን 1981 ያየነው መሰል ባህሪ ነው፣ በኢህአዴግ ዘመን መጠኑ ዝቅ ያለ ቢሆንም በ2001 አካባቢ መጠነኛ ፍላጎቶች ተንጸባርቀዋል። በእኛም ጊዜ በሰኔ 2010 16 ላይ ከለውጡ ሁለት ወር ሶስት ወር በኋላ መሰል ሙከራዎች በመስቀል አደባባይ ተካሂደዋል። እዚህ በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ ሁልጊዜም በሀይል ፍላጎትን ማሳካት፣ በሀይል ስልጣን ለመያዝ መሞከር፣ ሰው በመግደል ስልጣን ለመውረስ መሞከር ነበረ ማለት ነው።
"የሰኔ 15ቱም ከነዚህ ከላይ ከዘረዘርኳቸው ክስተቶች ለየት የሚያደርገው በክልል ደረጃ፣ በከተማ ደረጃ ዝቅ ብሎ ለመፈጸም የተሞከረ ሙከራ ነው። በክልል ደረጃ እንደዚህ ያለውን ጉዳይ ፈጽመህ ምን ታሳካለህ የሚለው ጉዳይ ቅድም ያልኩት የስሁት ግምገማ ውጤት አካል ይመስለኛል። እንዴት ታስታውሰዋለህ እንዴት ይታወሳል አልከው፣ የታሪካችን የጠባሳችን አካል አድርጌ ነው ማስታውሰው።"
- ጠቅላይ ሚ/ር ዐቢይ አህመድ
6 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) [የሰኔ 16ቱ ጉዳይ] የፖለቲካ ሴራ ተንታኞች መጠቀምያም ሆኗል። ታስታውስ ከሆነ እለቱ ቅዳሜ ነበር፣ ዊኬንድ ነበር፣ ማምሻ ላይ ነበር ይሄ ጉዳይ የተፈጠረው። እና እኔ እዚህ ቢሮ ቆይቼ ከቢሮ ስወጣ ነው መረጃው የሰማሁት። እና ለሚዲያ መነገር አለበት የሚል ሀሳብ መጥቶ የሚዲያ አካላት ይጠሩ ብለን ፋና፣ ኢቢሲ፣ አሚኮ ተጠርተው ነበር። መግለጫ የሰጠሁበትን ቦታ እስከዛሬ አስታውሰዋለሁ እኔ። ነገር ግን ፋና እና ኢቢሲ ምናልባትም ዊኬንድ ስለሆነ ምሽትም ስለነበረ ስንጠራቸው በዚያ ፍጥነት አልመጡልንም፣ አሚኮ ግን ጎረቤት ነው እዚህ 4 ኪሎ ነው መስሪያ ቤቱ፣ መኪናም ላያስፈልገው ይችላል - እዚሁ ስለሆነ። ልክ ጥሪው ሲደረግ ወዲያው አሚኮ መጣ፣ አሚኮ መጥቶ የተወሰነ ደቂቃ ጠበቀን እነዚያ ቢደርሱ ብለን፣ ዘገዩብን። እና መጨረሻ የመጣው ሀሳብ 'ምንም እኮ ችግር የለውም አሚኮ ወስዶ ለሁሉም ሊያከፋፍል ስለሚችል ለአሚኮ ይሰጥ ተብሎ እኔ ቤት ነው ለአሚኮ የሰጠሁት። በኋላ ግን ባህርዳር ላይ ሆኖ መግለጫ የሰጠው ወደሚል የሴራ ትንተና ተቀይሯል። እንደዚህ ያለው ከእውነት የተፋታ፣ ዛሬም ለነገም የማይበጅ፣ ውስጥህ እያወቀ የሚሸነገል፣ የሚዋሽ ነገር ጥፋት ብቻ ነው የሚያመጣው እና... ያ ክስተት ከመነሻው የሚሳካ ነው፣ ከመነሻው አንድ ግብ የሚያሟላ ነው ባትልም፣ እንደ ጥቁር ጠባሳ የሚወሰድ መጥፎ ክስተት ነው ብዬ ነው የማየው።"
ጠቅላይ ሚ/ር ዐቢይ አህመድ
ጠቅላይ ሚ/ር ዐቢይ አህመድ
6 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) በኢትዮጵያ ላለፉት ሶስት ዓመታት ሲካሄድ የቆየው ሀገራዊ የምክክር ሂደት አሁን ላይ ሀገሪቱን ክፉኛ ወደሚያወዛግቡ ፖለቲካዊ ጥያቄዎች መግባቱን ተከትሎ፣ ታዋቂው የኢኮኖሚ እና የፖለቲካ ተንታኝ አቶ ክቡር ገና የሂደቱን መነሻ ሀሳብ አጥብቀው ተቹ። አቶ ክቡር ዛሬ ባወጡት ጽሁፍ፣ ጉባኤው መጀመር የነበረበት "ኢትዮጵያውያን በጋራ መገንባት የሚፈልጉት የወደፊት ዕጣ ፈንታ ምንድን ነው?" በሚለው ጥያቄ ሆኖ ሳለ፣ ሂደቱ ግን "ኢትዮጵያውያንን የሚከፋፍላቸው ምንድን ነው?" በሚል የተሳሳተ የመነሻ ጥያቄ መጀመሩን አስምረውበታል።
የምክክር ኮሚሽኑ በአሁኑ ወቅት የሀገሪቱን ሰንደቅ ዓላማ፣ ምልክቶች፣ የወደፊቱን የህገ-መንግስት ቅርጽ፣ ፓርላማዊ ወይስ ፕሬዝዳንታዊ ስርዓት፣ የአዲስ አበባ አስተዳደር ባለቤትነት፣ የፌደራሊዝም፣ የማንነት፣ የታሪክ እና የስልጣን ጉዳዮችን ወደ ጠረጴዛ አምጥቷል። እነዚህ ጥያቄዎች እጅግ አስፈላጊ ቢሆኑም፣ ኢትዮጵያውያን በከፍተኛ ደረጃ የማይግባቡባቸው ጉዳዮች መሆናቸውን አቶ ክቡር ያስረዳሉ።
የፖለቲካ ፍልስፍና እንደሚያሳየው፣ ሀገራት በህገ-መንግስት ወይም በሰንደቅ ዓላማ ብቻ በአንድነት ሊቆሙ አይችሉም። ይልቁንም ህዝቦች ልዩነቶቻቸው እንደተጠበቁ ሆነው የጋራ መጻኢ ጊዜን ለመምረጥ ሲወስኑ ብቻ ነው ሀገራት ሊቀጥሉ የሚችሉት። ይህ ምርጫ ደግሞ ከህገ-መንግስት ቀረጻ በፊት ሊመጣ የሚገባው እንጂ በኋላ የሚመጣ አለመሆኑን ተንታኙ ይሞግታሉ። የምክክር ሂደቱ ግን ይህንን ተፈጥሯዊ ቅደም ተከተል የገለበጠው ይመስላል።
የምክክር ሂደቱ ዋነኛ ሀገራዊ ቅራኔዎችን በመለየት እና ተወካዮችን በማሰባሰብ መግባባት ላይ መድረስ ይቻላል የሚል ፍልስፍናን የተከተለ ይመስላል። ነገር ግን ታሪክ እንደሚያሳየው፣ ሰዎች ከጥልቅ ቅራኔዎቻቸው በመነሳት አንድነትን ሲያገኙ አይታይም፤ ይልቁንም የየራሳቸውን አቋም በበለጠ ሁኔታ መከላከልን ነው የሚማሩት። በታሪክ አተረጓጎም ክርክር የሚጀምር ውይይት፣ በተሻለ የተብራራ የታሪክ ልዩነትን በማስገኘት ያበቃል። ተሳታፊዎች ይበልጥ ተማምነው ሳይሆን፣ እርስ በርስ በተሻለ ሁኔታ ተረድተው ብቻ ሊወጡ ይችላሉ። አቶ ክቡር እንደሚሉት፣ መደማመጥ ማለት ሀገር መገንባት ማለት አይደለም።
የምክክር ሂደቱ የመጀመሪያ ምዕራፍ የህዝብን ብሶት ከመሰብሰብ ይልቅ የህዝብን ምኞት ማሰባሰብ ነበረበት። እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ኢትዮጵያ እንደ አንድ ሀገር ለምን መቀጠል እንዳለባት፣ ለየብቻ ሊገነባ የማይችል ነገር ግን በጋራ ሊገነባ የሚችል የወደፊት ጊዜ ምን እንደሆነ፣ እንዲሁም ለዚህ የጋራ ዕጣ ፈንታ ለመጠየቅ ሳይሆን ለመሰዋት ዝግጁ የሆነው ምን እንደሆነ ቢጠየቅ ኖሮ አቅጣጫው በተቀየረ ነበር። እነዚህ ጥያቄዎች ቢነሱ ኖሮ ውይይቱ ከባለቤትነት ይልቅ ወደ ዓላማ፣ ከመብት ይልቅ ወደ ኃላፊነት እንዲሁም ከትናንት ይልቅ ወደ ነገ በተሸጋገረ ነበር።
የሂደቱን ተአማኒነት አደጋ ላይ የሚጥለው ሌላው ትልቅ ፈተና፣ መሳተፍ የነበረባቸው ወሳኝ አካላት በጉባኤው ውስጥ አለመኖራቸው ነው። ታዋቂ የተቃዋሚ ፖለቲካ መሪዎች በእስር ላይ ይገኛሉ፣ አንዳንዶቹ በስደት ላይ ናቸው፣ ሌሎች ደግሞ በትጥቅ ትግል ውስጥ ተሳትፈዋል። ለኢትዮጵያ የተለየ ራዕይ ያላቸው በርካታ ተጽእኖ ፈጣሪ ምሁራን እና የፖለቲካ ተዋናዮች ሂደቱን እንደራሳቸው አድርገው አይመለከቱትም። ሰላም ብዙ ጊዜ የሚደራደረው አስቀድመው በሚግባቡ ሰዎች መካከል ሳይሆን፣ በመካከላቸው ጥልቅ ያለመተማመን ባለባቸው አካላት መካከል በመሆኑ፣ ወሳኝ ድምጽ ያላቸው አካላት ሁሉ በውጪ ከመቅረት ይልቅ በአዳራሹ ውስጥ መገኘታቸው እጅግ አስፈላጊ መሆኑን ጽሁፉ ያትታል።
ታሪክ የሚያስታውሰው ስንት ውይይቶች እንደተካሄዱ፣ ስንት አጀንዳዎች እንደተሰበሰቡ ወይም ስንት ሪፖርቶች እንደወጡ አይደለም። አቶ ክቡር ገና በመደምደሚያቸው እንዳሰፈሩት፣ ታሪክ የሚዘክረው "ምክክሩ የኢትዮጵያን የጋራ ብሔራዊ ማንነት አጠናክሯል ወይስ በቀላሉ የኢትዮጵያን አለመግባባቶች በተሻለ ሁኔታ አደራጅቷል?" የሚለውን ብቻ ነው። ተሳታፊዎች ከጉባኤው ሲወጡ "አሁን በጋራ ምን ዓይነት የወደፊት ጊዜ መገንባት እንችላለን?" ብለው ከጠየቁ፣ ሀገርን የመገን ባት እጅግ ወሳኝ ስራ ተጀምሯል ማለት ነው። ይህ ደግሞ የምክክር ጉባኤው ሊጀምርበት ይገባ የነበረው ትክክለኛው የመጀመሪያ ጥያቄ መሆን ነበረበት።
የምክክር ኮሚሽኑ በአሁኑ ወቅት የሀገሪቱን ሰንደቅ ዓላማ፣ ምልክቶች፣ የወደፊቱን የህገ-መንግስት ቅርጽ፣ ፓርላማዊ ወይስ ፕሬዝዳንታዊ ስርዓት፣ የአዲስ አበባ አስተዳደር ባለቤትነት፣ የፌደራሊዝም፣ የማንነት፣ የታሪክ እና የስልጣን ጉዳዮችን ወደ ጠረጴዛ አምጥቷል። እነዚህ ጥያቄዎች እጅግ አስፈላጊ ቢሆኑም፣ ኢትዮጵያውያን በከፍተኛ ደረጃ የማይግባቡባቸው ጉዳዮች መሆናቸውን አቶ ክቡር ያስረዳሉ።
የፖለቲካ ፍልስፍና እንደሚያሳየው፣ ሀገራት በህገ-መንግስት ወይም በሰንደቅ ዓላማ ብቻ በአንድነት ሊቆሙ አይችሉም። ይልቁንም ህዝቦች ልዩነቶቻቸው እንደተጠበቁ ሆነው የጋራ መጻኢ ጊዜን ለመምረጥ ሲወስኑ ብቻ ነው ሀገራት ሊቀጥሉ የሚችሉት። ይህ ምርጫ ደግሞ ከህገ-መንግስት ቀረጻ በፊት ሊመጣ የሚገባው እንጂ በኋላ የሚመጣ አለመሆኑን ተንታኙ ይሞግታሉ። የምክክር ሂደቱ ግን ይህንን ተፈጥሯዊ ቅደም ተከተል የገለበጠው ይመስላል።
የምክክር ሂደቱ ዋነኛ ሀገራዊ ቅራኔዎችን በመለየት እና ተወካዮችን በማሰባሰብ መግባባት ላይ መድረስ ይቻላል የሚል ፍልስፍናን የተከተለ ይመስላል። ነገር ግን ታሪክ እንደሚያሳየው፣ ሰዎች ከጥልቅ ቅራኔዎቻቸው በመነሳት አንድነትን ሲያገኙ አይታይም፤ ይልቁንም የየራሳቸውን አቋም በበለጠ ሁኔታ መከላከልን ነው የሚማሩት። በታሪክ አተረጓጎም ክርክር የሚጀምር ውይይት፣ በተሻለ የተብራራ የታሪክ ልዩነትን በማስገኘት ያበቃል። ተሳታፊዎች ይበልጥ ተማምነው ሳይሆን፣ እርስ በርስ በተሻለ ሁኔታ ተረድተው ብቻ ሊወጡ ይችላሉ። አቶ ክቡር እንደሚሉት፣ መደማመጥ ማለት ሀገር መገንባት ማለት አይደለም።
የምክክር ሂደቱ የመጀመሪያ ምዕራፍ የህዝብን ብሶት ከመሰብሰብ ይልቅ የህዝብን ምኞት ማሰባሰብ ነበረበት። እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ኢትዮጵያ እንደ አንድ ሀገር ለምን መቀጠል እንዳለባት፣ ለየብቻ ሊገነባ የማይችል ነገር ግን በጋራ ሊገነባ የሚችል የወደፊት ጊዜ ምን እንደሆነ፣ እንዲሁም ለዚህ የጋራ ዕጣ ፈንታ ለመጠየቅ ሳይሆን ለመሰዋት ዝግጁ የሆነው ምን እንደሆነ ቢጠየቅ ኖሮ አቅጣጫው በተቀየረ ነበር። እነዚህ ጥያቄዎች ቢነሱ ኖሮ ውይይቱ ከባለቤትነት ይልቅ ወደ ዓላማ፣ ከመብት ይልቅ ወደ ኃላፊነት እንዲሁም ከትናንት ይልቅ ወደ ነገ በተሸጋገረ ነበር።
የሂደቱን ተአማኒነት አደጋ ላይ የሚጥለው ሌላው ትልቅ ፈተና፣ መሳተፍ የነበረባቸው ወሳኝ አካላት በጉባኤው ውስጥ አለመኖራቸው ነው። ታዋቂ የተቃዋሚ ፖለቲካ መሪዎች በእስር ላይ ይገኛሉ፣ አንዳንዶቹ በስደት ላይ ናቸው፣ ሌሎች ደግሞ በትጥቅ ትግል ውስጥ ተሳትፈዋል። ለኢትዮጵያ የተለየ ራዕይ ያላቸው በርካታ ተጽእኖ ፈጣሪ ምሁራን እና የፖለቲካ ተዋናዮች ሂደቱን እንደራሳቸው አድርገው አይመለከቱትም። ሰላም ብዙ ጊዜ የሚደራደረው አስቀድመው በሚግባቡ ሰዎች መካከል ሳይሆን፣ በመካከላቸው ጥልቅ ያለመተማመን ባለባቸው አካላት መካከል በመሆኑ፣ ወሳኝ ድምጽ ያላቸው አካላት ሁሉ በውጪ ከመቅረት ይልቅ በአዳራሹ ውስጥ መገኘታቸው እጅግ አስፈላጊ መሆኑን ጽሁፉ ያትታል።
ታሪክ የሚያስታውሰው ስንት ውይይቶች እንደተካሄዱ፣ ስንት አጀንዳዎች እንደተሰበሰቡ ወይም ስንት ሪፖርቶች እንደወጡ አይደለም። አቶ ክቡር ገና በመደምደሚያቸው እንዳሰፈሩት፣ ታሪክ የሚዘክረው "ምክክሩ የኢትዮጵያን የጋራ ብሔራዊ ማንነት አጠናክሯል ወይስ በቀላሉ የኢትዮጵያን አለመግባባቶች በተሻለ ሁኔታ አደራጅቷል?" የሚለውን ብቻ ነው። ተሳታፊዎች ከጉባኤው ሲወጡ "አሁን በጋራ ምን ዓይነት የወደፊት ጊዜ መገንባት እንችላለን?" ብለው ከጠየቁ፣ ሀገርን የመገን ባት እጅግ ወሳኝ ስራ ተጀምሯል ማለት ነው። ይህ ደግሞ የምክክር ጉባኤው ሊጀምርበት ይገባ የነበረው ትክክለኛው የመጀመሪያ ጥያቄ መሆን ነበረበት።
Sponsored by
Surafel
6 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) 'እግረኛው' በተሰኘው የዩቲዩብ ቻናል የተለያዩ ግለሰቦችን ቃለ ምልልስ በማድረግ የሚታወቀው ጋዜጠኛ ተክለሀይማኖት አዳነ፣ እንዲሁም የሀገር መከላከያ ሰራዊት የደንብ ልብስ በመልበስ አከራካሪ መልዕክቶችን ሲያስተላልፍ የነበረው አበባየሁ ደሜ (አለማየሁ) በፌዴራል ፖሊስ ቁጥጥር ስር ዋሉ።
የፌዴራል ፖሊስ ጋዜጠኛ ተክለሀይማኖትን ዛሬ በፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አንደኛ የወንጀል ችሎት ያቀረበው ሲሆን፣ "ሀሰተኛ መረጃ በማሰራጨትና ፍትህን ለማዛባት በመሞከር" ወንጀል እንደጠረጠረው ለችሎቱ አስታውቋል። ፍርድ ቤቱም የፖሊስን የክስ መዝገብ ከመረመረ በኋላ፣ የቀረበለትን የጊዜ ቀጠሮ ጥያቄ በመቀበል ለሐምሌ 28 ቀን 2018 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል። በመሆኑም አቶ ተክለሀይማኖት እስከ ቀጠሮው ዕለት ድረስ በማረሚያ ቤት በእስር የሚቆይ ይሆናል።
የጋዜጠኛው በቁጥጥር ስር መዋል መነሻ ምክንያት በውል ባይታወቅም፣ በቅርቡ ከ'ፊንቴክ' (Fintech) የመኪና ማጭበርበር ጉዳይ ጋር በተያያዘ ክስ ከተመሰረተባቸው አርቲስቶች ጋር ያደረገውን ቃለ ምልልስ በሚዲያው በሁለት ክፍሎች ማሰራጨቱ ይታወሳል። በተጨማሪም የሀገር መከላከያ ሰራዊት ልብስ ለብሶ ከቀረበው ግለሰብ ጋር ያደረገው አነጋጋሪ ቃለ ምልልስ ለዚህ እስር መንስኤ ሊሆን እንደሚችል ቢገመትም፣ ጉዳዩ ከነዚሁ ስርጭቶች ጋር ይያያዝ አይያያዝ ዘ-ሐበሻ ማረጋገጥ አልቻለም።
በተያያዘ ዜና፣ በጋዜጠኛው ሚዲያ ላይ ቃለ ምልልስ የሰጠው ግለሰብም በቁጥጥር ስር መዋሉ ተገልጿል። የሀገር መከላከያ ሰራዊት አልባሳትን ያለአግባብ በመጠቀም በየማህበራዊ ሚዲያው የአንድነትና የፍቅር ሀሳብ ከማስተላለፍ ይልቅ የመከፋፈል ንግግሮችን እና አላስፈላጊ መልእክቶችን ሲያሰራጭ የነበረው አበባየሁ ደሜ በፖሊስ ተይዟል።
የፌዴራል ፖሊስ ጋዜጠኛ ተክለሀይማኖትን ዛሬ በፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አንደኛ የወንጀል ችሎት ያቀረበው ሲሆን፣ "ሀሰተኛ መረጃ በማሰራጨትና ፍትህን ለማዛባት በመሞከር" ወንጀል እንደጠረጠረው ለችሎቱ አስታውቋል። ፍርድ ቤቱም የፖሊስን የክስ መዝገብ ከመረመረ በኋላ፣ የቀረበለትን የጊዜ ቀጠሮ ጥያቄ በመቀበል ለሐምሌ 28 ቀን 2018 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል። በመሆኑም አቶ ተክለሀይማኖት እስከ ቀጠሮው ዕለት ድረስ በማረሚያ ቤት በእስር የሚቆይ ይሆናል።
የጋዜጠኛው በቁጥጥር ስር መዋል መነሻ ምክንያት በውል ባይታወቅም፣ በቅርቡ ከ'ፊንቴክ' (Fintech) የመኪና ማጭበርበር ጉዳይ ጋር በተያያዘ ክስ ከተመሰረተባቸው አርቲስቶች ጋር ያደረገውን ቃለ ምልልስ በሚዲያው በሁለት ክፍሎች ማሰራጨቱ ይታወሳል። በተጨማሪም የሀገር መከላከያ ሰራዊት ልብስ ለብሶ ከቀረበው ግለሰብ ጋር ያደረገው አነጋጋሪ ቃለ ምልልስ ለዚህ እስር መንስኤ ሊሆን እንደሚችል ቢገመትም፣ ጉዳዩ ከነዚሁ ስርጭቶች ጋር ይያያዝ አይያያዝ ዘ-ሐበሻ ማረጋገጥ አልቻለም።
በተያያዘ ዜና፣ በጋዜጠኛው ሚዲያ ላይ ቃለ ምልልስ የሰጠው ግለሰብም በቁጥጥር ስር መዋሉ ተገልጿል። የሀገር መከላከያ ሰራዊት አልባሳትን ያለአግባብ በመጠቀም በየማህበራዊ ሚዲያው የአንድነትና የፍቅር ሀሳብ ከማስተላለፍ ይልቅ የመከፋፈል ንግግሮችን እና አላስፈላጊ መልእክቶችን ሲያሰራጭ የነበረው አበባየሁ ደሜ በፖሊስ ተይዟል።
7 days ago
(ዘ-ሐበሻ ስፖርት) የኒውካስሉ ተወዳጅ የቀድሞ አሰልጣኝ ኬቨን ኪጋን ካረፉ ገና አስር ቀናት ብቻ ቢቆጠሩም፣ ክለቡ ሌላ ያልተጠበቀ መርዶ አስተናግዷል፦ የኪጋንን ህልም እውን በማድረግ ክለቡን ለክብር ያበቁት አሰልጣኝ ኤዲ ሃው ከኃላፊነታቸው መልቀቃቸውን ይፋ አድርገዋል።
ከእጅግ አስከፊው የ2025-26 የውድድር ዘመን በኋላ በኃላፊነታቸው ለመቀጠል እና ክለቡን መልሰው ለመገንባት ቃል ገብተው የነበሩት ኤዲ ሃው፣ አዲሱ የፕሪሚየር ሊግ የውድድር ዘመን ሊጀመር ሶስት ሳምንታት ብቻ ሲቀሩት ውሳኔያቸውን ቀልብሰዋል።
ማክሰኞ ምሽት በቅድመ-ውድድር ዝግጅት ኒውካስል ከብሪስቶል ሲቲ ጋር ባደረገው የወዳጅነት ጨዋታ 4-1 በሆነ አሳፋሪ ውጤት መሸነፉ ብዙ ነገሮችን የቀየረ ይመስላል። ከሜዳቸው ውጪ ስታዲየሙን ሞልተው የነበሩት የኒውካስል ደጋፊዎች ያሰሙት የተቃውሞ እና የቁጣ ድምፅ፣ ይህ "ትርጉም አልባ" የሚመስል የወዳጅነት ጨዋታ ትልቅ መዘዝ ይዞ እንደሚመጣ አመላካች ነበር።
በማግስቱ ረቡዕ ጠዋት እንደተሰማው ኤዲ ሃው ኃላፊነታቸውን ለመልቀቅ ወስነዋል። የቅርብ ምንጮች እንደሚያሳዩት ይህ ውሳኔ የቅጽበት የብስጭት ውሳኔ ሳይሆን፣ ከከባዱ የውድድር ዘመን መገባደጃ አንስቶ አሰልጣኙ በውስጣቸው ሲያብሰለስሉት የቆዩት እና ሊሸከሙት ያልቻሉት ከባድ ሸክም ውጤት ነው።
ለኤዲ ሃው፣ ይህ ስንብት እጅግ አስደናቂ ለነበረው የኒውካስል ቆይታቸው የማይመጥን አሳዛኝ ማብቂያ ነው። ከ30 ዓመታት በፊት ኬቨን ኪጋን እጅግ ተቃርበውት የነበረውን፣ ደጋፊውም ለ70 ዓመታት ሲናፍቀው የነበረውን ትልቅ ዋንጫ ወደ ሴንት ጀምስ ፓርክ ያመጡት እርሳቸው ነበሩ።
እ.ኤ.አ በ2021 ክለቡ በፕሪሚየር ሊጉ 19ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጦ ወደ መውረድ አፋፍ በደረሰበት ወቅት ኃላፊነቱን የተረከቡት ሃው፣ ኒውካስልን በሊጉ ማቆየት ብቻ ሳይሆን በሚቀጥለው ዓመት ወደ ቻምፒዮንስ ሊግ መድረክ መልሰውታል። በ2024-25 ደግሞ በካራባኦ ካፕ የፍጻሜ ጨዋታ የሊጉን ሻምፒዮን ሊቨርፑልን በዌምብሌይ አሸንፈው ታሪካዊ ዋንጫ በማንሳት ስማቸውን በኒውካስል ታሪክ በወርቅ ቀለም አጽፈው ነበር።
ይህ የዋንጫ ድል የሳዑዲው የኢንቨስትመንት ፈንድ (PIF) በባለቤትነት ለሚያስተዳድረው እና የፕሪሚየር ሊጉን ዋንጫ ለሚያልመው ኒውካስል እንደ ትልቅ መነሻ መታየት ነበረበት። ሆኖም፣ የ2025ቱ ክረምት የሁሉንም ነገር አቅጣጫ ቀየረው።
በተለይም አሌክሳንደር ኢሳክን በክለቡ ለማቆየት የተደረገው ተስፋ አስቆራጭ እና መራር ትግል፣ በመጨረሻም ስዊድናዊው አጥቂ በብሪታንያ የዝውውር ሪከርድ በዝውውር መስኮቱ መዘጋጃ ዕለት ወደ ሊቨርፑል ማምራቱ ክለቡን ክፉኛ ጎድቶታል። ኒውካስል የኢሳክን ክፍተት ሊተካ የሚችል ተጫዋች ማምጣት አልቻለም። እንደ ሁጎ ኤኪቲኬ፣ ቤንጃሚን ሴስኮ እና ጆአዎ ፔድሮ ያሉ ታላላቅ ኢላማዎቹን ለተቀናቃኝ የፕሪሚየር ሊግ ክለቦች አሳልፎ ሰጠ።
በምትኩ ክለቡ እና ኤዲ ሃው በጋራ ያመጧቸው ኒክ ዎልቴማዴ፣ ዮአን ዊሳ እና አንቶኒ ኤላንጋ አጠቃላይ 180 ሚሊዮን ፓውንድ ($243m) ቢወጣባቸውም፣ ያሳዩት አቋም እና የገጠማቸው የጉዳት ችግር የተከፈለባቸውን ዋጋ ፈጽሞ ሊያጸድቅ አልቻለም። የኤላንጋ እና ዎልቴማዴ ብቃት ሲዋዥቅ፣ አጥቂው ዊሳ በሙሉ የውድድር ዘመኑ በሊጉ ያስቆጠረው አንድ ጎል ብቻ ነበር። በ43 ሚሊዮን ፓውንድ የመጣው ጃኮብ ራምሴይም በቁርጭምጭሚት ጉዳት ሲሰቃይ ጊዜውን አሳልፏል።
የዝውውር ውድቀቱ በሜዳ ላይ ውጤት ቢሸፈን ኖሮ የኤዲ ሃው ጫና ያን ያህል አይከፋም ነበር። ሆኖም የ2025-26 የውድድር ዘመን ለኒውካስል እውነተኛ ቅዠት ሆኖ አለፈ።
በዓመቱ መጀመሪያ ጥሩ አጀማመር ያሳየው ክለቡ፣ ከአዲሱ ዓመት በኋላ ግን የመውረድ ስጋት ወዳለባቸው ቡድኖች ወረደ። ከጥር መጨረሻ አንስቶ እስከ የውድድር ዘመኑ ማብቂያ ድረስ ካደረጋቸው 16 ጨዋታዎች በ10ሩ በመሸነፉ፣ ከ6ኛ ደረጃ ወደ 12ኛ ደረጃ በማሽቆልቆል ደጋፊውን በሀዘን እና በቁጣ ሞላው።
ይባስ ብሎ በኤፍኤ ካፕ እና በካራባኦ ካፕ በማንችስተር ሲቲ በቀላሉ ሲሰናበት፣ በቻምፒዮንስ ሊጉ ደግሞ ባርሴሎና በድምር ውጤት 8-3 በሆነ አሳፋሪ የጎል ናዳ አዋርዶ ከውድድሩ አስወጣው።
የኤዲ ሃው የወደፊት እጣ ፈንታ ጥያቄ ውስጥ የገባው ገና በጊዜ ነበር። በሚያዝያ ወር ኒውካስል በተከታታይ ለሶስተኛ ጊዜ በቦርንማውዝ ከተሸነፈ በኋላ፣ የክለቡ ታሪካዊ ሌጀንድ አላን ሺረር እንዲህ ብሎ ነበር፦ "ለኤዲ ምን ያህል ከባድ ጊዜ እንደሆነ ባውቅም፣ የወደፊት እጣ ፈንታው ምን እንደሚሆን አላውቅም። ዳግም የመዋጋት እና ክለቡን የማንሳት አቅሙ ያለው አይመስለኝም። በሚቀጥለው የውድድር ዘመን ኤዲ ሃው ኒውካስልን ያሰለጥናል ብዬ አላስብም።"
ሺረር እንዳለውም ሆነ ኤዲ ሃው ኒውካስልን ወደ ቀደመ ክብሩ የመመለስ ትልቅ ታሪክ ሰርተው፣ ነገር ግን በኋለኛው አመታቸው በዝውውር ውድቀት እና በሜዳ ላይ አስከፊ ውጤቶች ታጅበው የሴንት ጀምስ ፓርኩን በር ዘግተው ወጥተዋል።
ከእጅግ አስከፊው የ2025-26 የውድድር ዘመን በኋላ በኃላፊነታቸው ለመቀጠል እና ክለቡን መልሰው ለመገንባት ቃል ገብተው የነበሩት ኤዲ ሃው፣ አዲሱ የፕሪሚየር ሊግ የውድድር ዘመን ሊጀመር ሶስት ሳምንታት ብቻ ሲቀሩት ውሳኔያቸውን ቀልብሰዋል።
ማክሰኞ ምሽት በቅድመ-ውድድር ዝግጅት ኒውካስል ከብሪስቶል ሲቲ ጋር ባደረገው የወዳጅነት ጨዋታ 4-1 በሆነ አሳፋሪ ውጤት መሸነፉ ብዙ ነገሮችን የቀየረ ይመስላል። ከሜዳቸው ውጪ ስታዲየሙን ሞልተው የነበሩት የኒውካስል ደጋፊዎች ያሰሙት የተቃውሞ እና የቁጣ ድምፅ፣ ይህ "ትርጉም አልባ" የሚመስል የወዳጅነት ጨዋታ ትልቅ መዘዝ ይዞ እንደሚመጣ አመላካች ነበር።
በማግስቱ ረቡዕ ጠዋት እንደተሰማው ኤዲ ሃው ኃላፊነታቸውን ለመልቀቅ ወስነዋል። የቅርብ ምንጮች እንደሚያሳዩት ይህ ውሳኔ የቅጽበት የብስጭት ውሳኔ ሳይሆን፣ ከከባዱ የውድድር ዘመን መገባደጃ አንስቶ አሰልጣኙ በውስጣቸው ሲያብሰለስሉት የቆዩት እና ሊሸከሙት ያልቻሉት ከባድ ሸክም ውጤት ነው።
ለኤዲ ሃው፣ ይህ ስንብት እጅግ አስደናቂ ለነበረው የኒውካስል ቆይታቸው የማይመጥን አሳዛኝ ማብቂያ ነው። ከ30 ዓመታት በፊት ኬቨን ኪጋን እጅግ ተቃርበውት የነበረውን፣ ደጋፊውም ለ70 ዓመታት ሲናፍቀው የነበረውን ትልቅ ዋንጫ ወደ ሴንት ጀምስ ፓርክ ያመጡት እርሳቸው ነበሩ።
እ.ኤ.አ በ2021 ክለቡ በፕሪሚየር ሊጉ 19ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጦ ወደ መውረድ አፋፍ በደረሰበት ወቅት ኃላፊነቱን የተረከቡት ሃው፣ ኒውካስልን በሊጉ ማቆየት ብቻ ሳይሆን በሚቀጥለው ዓመት ወደ ቻምፒዮንስ ሊግ መድረክ መልሰውታል። በ2024-25 ደግሞ በካራባኦ ካፕ የፍጻሜ ጨዋታ የሊጉን ሻምፒዮን ሊቨርፑልን በዌምብሌይ አሸንፈው ታሪካዊ ዋንጫ በማንሳት ስማቸውን በኒውካስል ታሪክ በወርቅ ቀለም አጽፈው ነበር።
ይህ የዋንጫ ድል የሳዑዲው የኢንቨስትመንት ፈንድ (PIF) በባለቤትነት ለሚያስተዳድረው እና የፕሪሚየር ሊጉን ዋንጫ ለሚያልመው ኒውካስል እንደ ትልቅ መነሻ መታየት ነበረበት። ሆኖም፣ የ2025ቱ ክረምት የሁሉንም ነገር አቅጣጫ ቀየረው።
በተለይም አሌክሳንደር ኢሳክን በክለቡ ለማቆየት የተደረገው ተስፋ አስቆራጭ እና መራር ትግል፣ በመጨረሻም ስዊድናዊው አጥቂ በብሪታንያ የዝውውር ሪከርድ በዝውውር መስኮቱ መዘጋጃ ዕለት ወደ ሊቨርፑል ማምራቱ ክለቡን ክፉኛ ጎድቶታል። ኒውካስል የኢሳክን ክፍተት ሊተካ የሚችል ተጫዋች ማምጣት አልቻለም። እንደ ሁጎ ኤኪቲኬ፣ ቤንጃሚን ሴስኮ እና ጆአዎ ፔድሮ ያሉ ታላላቅ ኢላማዎቹን ለተቀናቃኝ የፕሪሚየር ሊግ ክለቦች አሳልፎ ሰጠ።
በምትኩ ክለቡ እና ኤዲ ሃው በጋራ ያመጧቸው ኒክ ዎልቴማዴ፣ ዮአን ዊሳ እና አንቶኒ ኤላንጋ አጠቃላይ 180 ሚሊዮን ፓውንድ ($243m) ቢወጣባቸውም፣ ያሳዩት አቋም እና የገጠማቸው የጉዳት ችግር የተከፈለባቸውን ዋጋ ፈጽሞ ሊያጸድቅ አልቻለም። የኤላንጋ እና ዎልቴማዴ ብቃት ሲዋዥቅ፣ አጥቂው ዊሳ በሙሉ የውድድር ዘመኑ በሊጉ ያስቆጠረው አንድ ጎል ብቻ ነበር። በ43 ሚሊዮን ፓውንድ የመጣው ጃኮብ ራምሴይም በቁርጭምጭሚት ጉዳት ሲሰቃይ ጊዜውን አሳልፏል።
የዝውውር ውድቀቱ በሜዳ ላይ ውጤት ቢሸፈን ኖሮ የኤዲ ሃው ጫና ያን ያህል አይከፋም ነበር። ሆኖም የ2025-26 የውድድር ዘመን ለኒውካስል እውነተኛ ቅዠት ሆኖ አለፈ።
በዓመቱ መጀመሪያ ጥሩ አጀማመር ያሳየው ክለቡ፣ ከአዲሱ ዓመት በኋላ ግን የመውረድ ስጋት ወዳለባቸው ቡድኖች ወረደ። ከጥር መጨረሻ አንስቶ እስከ የውድድር ዘመኑ ማብቂያ ድረስ ካደረጋቸው 16 ጨዋታዎች በ10ሩ በመሸነፉ፣ ከ6ኛ ደረጃ ወደ 12ኛ ደረጃ በማሽቆልቆል ደጋፊውን በሀዘን እና በቁጣ ሞላው።
ይባስ ብሎ በኤፍኤ ካፕ እና በካራባኦ ካፕ በማንችስተር ሲቲ በቀላሉ ሲሰናበት፣ በቻምፒዮንስ ሊጉ ደግሞ ባርሴሎና በድምር ውጤት 8-3 በሆነ አሳፋሪ የጎል ናዳ አዋርዶ ከውድድሩ አስወጣው።
የኤዲ ሃው የወደፊት እጣ ፈንታ ጥያቄ ውስጥ የገባው ገና በጊዜ ነበር። በሚያዝያ ወር ኒውካስል በተከታታይ ለሶስተኛ ጊዜ በቦርንማውዝ ከተሸነፈ በኋላ፣ የክለቡ ታሪካዊ ሌጀንድ አላን ሺረር እንዲህ ብሎ ነበር፦ "ለኤዲ ምን ያህል ከባድ ጊዜ እንደሆነ ባውቅም፣ የወደፊት እጣ ፈንታው ምን እንደሚሆን አላውቅም። ዳግም የመዋጋት እና ክለቡን የማንሳት አቅሙ ያለው አይመስለኝም። በሚቀጥለው የውድድር ዘመን ኤዲ ሃው ኒውካስልን ያሰለጥናል ብዬ አላስብም።"
ሺረር እንዳለውም ሆነ ኤዲ ሃው ኒውካስልን ወደ ቀደመ ክብሩ የመመለስ ትልቅ ታሪክ ሰርተው፣ ነገር ግን በኋለኛው አመታቸው በዝውውር ውድቀት እና በሜዳ ላይ አስከፊ ውጤቶች ታጅበው የሴንት ጀምስ ፓርኩን በር ዘግተው ወጥተዋል።
7 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በይፋዊ መግለጫቸው በተያያዘው ግህግ.jpeg ሰነድ ላይ) እንዳስታወቁት፣ 'የሰላም ቦርድ' ሀማስን ጨምሮ በጋዛ የሚገኙ ሁሉንም ታጣቂ ቡድኖች ሙሉ በሙሉ ትጥቅ ለማስፈታት የሚያስችል ታሪካዊ ስምምነት ላይ ደርሷል። ይህ ስምምነት ዘላቂ ሰላም እና ደህንነትን ለማረጋገጥ የተወሰደ እጅግ ትልቅ እና ወሳኝ እርምጃ መሆኑን ፕሬዝዳንቱ ገልጸዋል።
ስምምነቱ ጋዛ ከሰላም ቦርዱ ጋር በቅርበት በመስራት የፍልስጤምን ህዝብ በሚያግዝ አዲስ የፍልስጤም መንግስት እንድትተዳደር የሚያስችል ወሳኝ ምዕራፍ ነው። በሌላ በኩል ደግሞ ጋዛ ዳግም የሽብር ጥቃቶች መነሻ መሆኗ ስለሚያበቃ፣ እስራኤል የሚገባትን ደህንነት እንደምታገኝ በመግለጫው ተጠቁሟል። ይህ እርምጃ የትራምፕን 'ባለ 20-ነጥብ የሰላም እቅድ' ተግባራዊ ለማድረግ የተመዘገበ ትልቅ ስኬት መሆኑም ተብራርቷል።
የስምምነቱ ትግበራ በጥንቃቄ በተዋቀሩ ደረጃዎች የሚከናወን ይሆናል። የትጥቅ ማስፈታት ሂደቱ ሲጠናቀቅ የእስራኤል ጦር ከጋዛ የሚወጣ ሲሆን፣ ዓለም አቀፍ የማረጋጋት ኃይል ከአዲሱ የፍልስጤም ፖሊስ ኃይል ጋር በመተባበር የጋዛን እና የጎረቤቶቿን ነዋሪዎች ደህንነት የማረጋገጥ ኃላፊነት ይወስዳል።
ፕሬዝዳንት ትራምፕ መግለጫቸውን ሲቀጥሉ ከአንድ ዓመት በፊት ከነበረው አውዳሚ ጦርነት፣ ከባድ ሰብዓዊ ቀውስ እና ታጋቾች በጭካኔ በተያዙበት ሁኔታ አንጻር ሲታይ ዛሬ ላይ ታሪካዊ መሻሻል መታየቱን አውስተው፣ አሁንም ግን ብዙ ሊሰሩ የሚገባቸው ስራዎች መኖራቸውን አሳስበዋል። ለዚህ ታሪካዊ ስኬት መገኘት ከፍተኛ ጥረት ላደረጉት አሸማጋይ ሀገራት ማለትም ለግብፅ፣ ለኳታር እና ለቱርክ፣ እንዲሁም ያለመታከት ለሰራው የራሳቸው የልዑካን ቡድን የላቀ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
በጥቅምት 7 ከጋዛ የተነሳው ስጋት ዳግም እራሱን እንዳይገነባ ጥብቅ አቋም የተያዘበት ይህ ስምምነት፣ ጋዛን በመጨረሻ ህዝቧን ለሚያገለግል አዲስ የፍልስጤም መንግስት የሚያስረክብ መሆኑ ተረጋግጧል። በመጨረሻም ፕሬዝዳንት ትራምፕ ማንም ሊሳካ አይችልም ተብሎ ይታሰብ በነበረው በዚህ አስደናቂ እድገት ለሁሉም የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት በማስተላለፍ መግለጫቸውን አጠናቀዋል።
ስምምነቱ ጋዛ ከሰላም ቦርዱ ጋር በቅርበት በመስራት የፍልስጤምን ህዝብ በሚያግዝ አዲስ የፍልስጤም መንግስት እንድትተዳደር የሚያስችል ወሳኝ ምዕራፍ ነው። በሌላ በኩል ደግሞ ጋዛ ዳግም የሽብር ጥቃቶች መነሻ መሆኗ ስለሚያበቃ፣ እስራኤል የሚገባትን ደህንነት እንደምታገኝ በመግለጫው ተጠቁሟል። ይህ እርምጃ የትራምፕን 'ባለ 20-ነጥብ የሰላም እቅድ' ተግባራዊ ለማድረግ የተመዘገበ ትልቅ ስኬት መሆኑም ተብራርቷል።
የስምምነቱ ትግበራ በጥንቃቄ በተዋቀሩ ደረጃዎች የሚከናወን ይሆናል። የትጥቅ ማስፈታት ሂደቱ ሲጠናቀቅ የእስራኤል ጦር ከጋዛ የሚወጣ ሲሆን፣ ዓለም አቀፍ የማረጋጋት ኃይል ከአዲሱ የፍልስጤም ፖሊስ ኃይል ጋር በመተባበር የጋዛን እና የጎረቤቶቿን ነዋሪዎች ደህንነት የማረጋገጥ ኃላፊነት ይወስዳል።
ፕሬዝዳንት ትራምፕ መግለጫቸውን ሲቀጥሉ ከአንድ ዓመት በፊት ከነበረው አውዳሚ ጦርነት፣ ከባድ ሰብዓዊ ቀውስ እና ታጋቾች በጭካኔ በተያዙበት ሁኔታ አንጻር ሲታይ ዛሬ ላይ ታሪካዊ መሻሻል መታየቱን አውስተው፣ አሁንም ግን ብዙ ሊሰሩ የሚገባቸው ስራዎች መኖራቸውን አሳስበዋል። ለዚህ ታሪካዊ ስኬት መገኘት ከፍተኛ ጥረት ላደረጉት አሸማጋይ ሀገራት ማለትም ለግብፅ፣ ለኳታር እና ለቱርክ፣ እንዲሁም ያለመታከት ለሰራው የራሳቸው የልዑካን ቡድን የላቀ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
በጥቅምት 7 ከጋዛ የተነሳው ስጋት ዳግም እራሱን እንዳይገነባ ጥብቅ አቋም የተያዘበት ይህ ስምምነት፣ ጋዛን በመጨረሻ ህዝቧን ለሚያገለግል አዲስ የፍልስጤም መንግስት የሚያስረክብ መሆኑ ተረጋግጧል። በመጨረሻም ፕሬዝዳንት ትራምፕ ማንም ሊሳካ አይችልም ተብሎ ይታሰብ በነበረው በዚህ አስደናቂ እድገት ለሁሉም የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት በማስተላለፍ መግለጫቸውን አጠናቀዋል።
7 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ህገ-መንግስት ከጸደቀ 30 ዓመታት ቢቆጠሩም፣ ሀገሪቱ አሁንም የሰዎችን ህይወት ከሚቀጥፉ፣ ማህበረሰብን ከሚያፈናቅሉ እና የህዝብን አመኔታ ከሚሸረሽሩ ተደጋጋሚ ግጭቶች መላቀቅ አልቻለችም። አብዛኛዎቹ ሰዎች ለእነዚህ ችግሮች የብሔር ወይም የፖለቲካ ፉክክርን በዋነኛነት ቢወቅሱም፣ የፖለቲካ ትንታኔዎች ግን ዋነኛው እና ስር የሰደደው ችግር የፌደራል እና የክልል መንግስታት የጸጥታ ኃላፊነት ድንበር በህገ-መንግስቱ ላይ በግልጽ አለመቀመጡ መሆኑን ያመላክታሉ።
ይህ ግልጽነት የጎደለው አሰራር "የተበታተነ ሉዓላዊነት" ፈጥሯል። ይህም ማለት የተለያዩ የመንግስት እርከኖች በተደራረበ ህጋዊ ስልጣን እና እርስ በርስ በሚፎካከር ፖለቲካዊ ፍላጎት የጸጥታ ኃይልን ያዛሉ። በዚህም ምክንያት የፌደራል እና የክልል የጸጥታ መዋቅሮች ተደጋግፈው ከመስራት ይልቅ፣ አንዳንዴ በትይዩ አልያም በፉክክር መንፈስ ሲንቀሳቀሱ ይታያሉ፤ ይህም ግጭትን ለመከላከል የሚደረገውን ጥረት አወሳስቦታል።
የዚህ አጣብቂኝ መነሻ ያለው እ.ኤ.አ. በ1995 በጸደቀው የኢትዮጵያ ህገ-መንግስት ውስጥ ነው። ህገ-መንግስቱ የሀገር መከላከያ እና የፌደራል ፖሊስን ኃላፊነት ለፌደራል መንግስቱ በአንቀጽ 51(6) ስር ሲሰጥ፣ በሌላ በኩል ደግሞ ክልሎች የራሳቸውን ፖሊስ ኃይል እንዲያቋቁሙ እና ጸጥታ እንዲያስከብሩ በአንቀጽ 52(2)(g) ላይ ስልጣን ይሰጣቸዋል። ይህ ድንጋጌ የክልሎችን ራስን በራስ የማስተዳደር መብት እና የሀገርን አንድነት ለማመጣጠን የታለመ ቢሆንም፣ የክልል የፖሊስ ስልጣን የት ላይ ያበቃል የፌደራል የጸጥታ ኃላፊነትስ የት ይጀምራል ለሚለው መሰረታዊ ጥያቄ ምላሽ ሳይሰጥ ቀርቷል።
በዚህም ምክንያት ሁለት ተቋማዊ ድክመቶች ተፈጥረዋል። የመጀመሪያው፣ ክልሎች የተሰጣቸውን የፖሊስ ኃይል የማቋቋም መብት በመጠቀም ከመደበኛ የፖሊስ ግዳጅ ባለፈ ወታደራዊ ቅርጽ እና ትጥቅ ያላቸውን የክልል ልዩ ኃይሎችን ማቋቋማቸው ነው። ሁለተኛው ደግሞ፣ በክልሎች መካከል የሚነሱ የድንበር እና የማንነት ጥያቄዎችን የሚፈታ ጠንካራ ተቋማዊ አሰራር ባለመኖሩ የክልል ፖሊስ ተቋማት የፖለቲካው አካል በመሆን ግጭቶችን ከማብረድ ይልቅ ተሳታፊ ወደ መሆን መሸጋገራቸው ነው።
ህገ-መንግስታዊ ክፍተት ብቻውን ብጥብጥ አያመጣም። ነገር ግን ፖለቲከኞች የጸጥታ ኃላፊነቶች በተደራረቡበት ስርዓት ውስጥ ሲንቀሳቀሱ አደገኛ ይሆናል። በኢትዮጵያ፣ አንዱ የመንግስት እርከን ለራሱ ደህንነት ሲል የሚወስደው ራስን የመከላከል እርምጃ፣ በሌላው ወገን እንደ ትንኮሳ እና ለጥቃት እንደመዘጋጀት ይቆጠራል።
ይህ ተለዋዋጭ ሁኔታ በሚያዝያ 2015 ዓ.ም. የፌደራል መንግስት የክልል ልዩ ኃይሎችን መልሶ ለማደራጀት በወሰደው እርምጃ ወቅት በግልጽ ታይቷል። መንግስት እርምጃውን የተዋሃደ ሀገራዊ የጸጥታ መዋቅር ለመገንባት ያለመ መሆኑን ቢገልጽም፣ በተለይም በአማራ ክልል ከፍተኛ ፖለቲካዊ ተቃውሞን እና ቀጣይነት ያለውን ግጭት አስከትሏል። ይህ የሚያሳየው፣ የክልል መንግስታት የጸጥታ ተቋሞቻቸውን እንደ ህገ-መንግስታዊ የራስ ገዝ አስተዳደር መገለጫ አድርገው በሚያዩበት ፌደራላዊ ስርዓት ውስጥ፣ ኃይልን ማዕከላዊ ለማድረግ የሚደረግ ማንኛውም ሙከራ እንደ ፖለቲካዊ ጣልቃ ገብነት እንደሚቆጠር ነው።
መዋቅራዊ መፍትሄዎች፡ ኃይልን ብቻ ሳይሆን ህጉን ማስተካከል
የኢትዮጵያን ተደጋጋሚ የጸጥታ ቀውሶች በዘላቂነት ለመፍታት የተለያዩ መዋቅራዊ ማሻሻያዎችን ማድረግ የግድ ይላል። በቅድሚያ በአንቀጽ 51 እና በአንቀጽ 52 መካከል ያለውን የፌደራል እና የክልል የጸጥታ ኃላፊነቶች ግንኙነት በግልጽ በማብራራት የፌደራል መንግስት በምን ዓይነት ሁኔታዎች ውስጥ ጣልቃ መግባት እንዳለበት ህጋዊ ድንበር ሊቀመጥ ይገባል። በተጨማሪም የክልልን ራስን በራስ የማስተዳደር መብት በማይጋፋ መልኩ፣ መረጃ የሚለዋወጡበት እና ግጭቶች ወደ ጦርነት ከማምራታቸው በፊት የሚፈቱበት ቋሚ የፌደራል እና የክልል የጸጥታ ማስተባበሪያ መዋቅር መገንባት ያስፈልጋል።
በሌላ በኩል የፖሊስ ተቋማት ከፖለቲካ ወገንተኝነት የጸዱ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ እና በፖለቲካ የተነሳሱ የጸጥታ ጥሰቶችን የሚመረምር ገለልተኛ የቁጥጥር አካል በማቋቋም ተቋማዊ ተጠያቂነትን ማረጋገጥ ወሳኝ እርምጃ ነው። እንዲሁም የክልል ፖሊሶች ለክልል ፖለቲካዊ ፍላጎቶች ሳይሆን ለህገ-መንግስቱ እና ለህግ የበላይነት ታማኝ የሚሆኑበትን የጋራ ስልጠና እና ኦፕሬሽናል መርሆች በመተግበር የጋራ ፕሮፌሽናል አስተምህሮ ማዳበር ይገባል።
የኢትዮጵያ ተደጋጋሚ የጸጥታ ቀውሶች የሚያሳዩት "ህገ-መንግስታዊ ንድፍ ልክ እንደ ፖለቲካዊ አመራር ሁሉ እጅግ ወሳኝ መሆኑን" ነው። ዘላቂ ሰላም ጊዜያዊ ተኩስ አቁምን ወይም ወቅታዊ የጸጥታ ዘመቻዎችን ብቻ ተመርኩዞ ሊመጣ አይችልም። የኢትዮጵያ ማዕከላዊ ጥያቄ የጸጥታ ማሻሻያ ያስፈልጋል ወይ የሚለው ሳይሆን፣ ማሻሻያው የችግሩን ውጫዊ ምልክቶች ብቻ ሳይሆን ተቋማዊ እና ህገ-መንግስታዊ ስር-መሰረቱን ይፈታል ወይ የሚለው ነው።
ይህ ግልጽነት የጎደለው አሰራር "የተበታተነ ሉዓላዊነት" ፈጥሯል። ይህም ማለት የተለያዩ የመንግስት እርከኖች በተደራረበ ህጋዊ ስልጣን እና እርስ በርስ በሚፎካከር ፖለቲካዊ ፍላጎት የጸጥታ ኃይልን ያዛሉ። በዚህም ምክንያት የፌደራል እና የክልል የጸጥታ መዋቅሮች ተደጋግፈው ከመስራት ይልቅ፣ አንዳንዴ በትይዩ አልያም በፉክክር መንፈስ ሲንቀሳቀሱ ይታያሉ፤ ይህም ግጭትን ለመከላከል የሚደረገውን ጥረት አወሳስቦታል።
የዚህ አጣብቂኝ መነሻ ያለው እ.ኤ.አ. በ1995 በጸደቀው የኢትዮጵያ ህገ-መንግስት ውስጥ ነው። ህገ-መንግስቱ የሀገር መከላከያ እና የፌደራል ፖሊስን ኃላፊነት ለፌደራል መንግስቱ በአንቀጽ 51(6) ስር ሲሰጥ፣ በሌላ በኩል ደግሞ ክልሎች የራሳቸውን ፖሊስ ኃይል እንዲያቋቁሙ እና ጸጥታ እንዲያስከብሩ በአንቀጽ 52(2)(g) ላይ ስልጣን ይሰጣቸዋል። ይህ ድንጋጌ የክልሎችን ራስን በራስ የማስተዳደር መብት እና የሀገርን አንድነት ለማመጣጠን የታለመ ቢሆንም፣ የክልል የፖሊስ ስልጣን የት ላይ ያበቃል የፌደራል የጸጥታ ኃላፊነትስ የት ይጀምራል ለሚለው መሰረታዊ ጥያቄ ምላሽ ሳይሰጥ ቀርቷል።
በዚህም ምክንያት ሁለት ተቋማዊ ድክመቶች ተፈጥረዋል። የመጀመሪያው፣ ክልሎች የተሰጣቸውን የፖሊስ ኃይል የማቋቋም መብት በመጠቀም ከመደበኛ የፖሊስ ግዳጅ ባለፈ ወታደራዊ ቅርጽ እና ትጥቅ ያላቸውን የክልል ልዩ ኃይሎችን ማቋቋማቸው ነው። ሁለተኛው ደግሞ፣ በክልሎች መካከል የሚነሱ የድንበር እና የማንነት ጥያቄዎችን የሚፈታ ጠንካራ ተቋማዊ አሰራር ባለመኖሩ የክልል ፖሊስ ተቋማት የፖለቲካው አካል በመሆን ግጭቶችን ከማብረድ ይልቅ ተሳታፊ ወደ መሆን መሸጋገራቸው ነው።
ህገ-መንግስታዊ ክፍተት ብቻውን ብጥብጥ አያመጣም። ነገር ግን ፖለቲከኞች የጸጥታ ኃላፊነቶች በተደራረቡበት ስርዓት ውስጥ ሲንቀሳቀሱ አደገኛ ይሆናል። በኢትዮጵያ፣ አንዱ የመንግስት እርከን ለራሱ ደህንነት ሲል የሚወስደው ራስን የመከላከል እርምጃ፣ በሌላው ወገን እንደ ትንኮሳ እና ለጥቃት እንደመዘጋጀት ይቆጠራል።
ይህ ተለዋዋጭ ሁኔታ በሚያዝያ 2015 ዓ.ም. የፌደራል መንግስት የክልል ልዩ ኃይሎችን መልሶ ለማደራጀት በወሰደው እርምጃ ወቅት በግልጽ ታይቷል። መንግስት እርምጃውን የተዋሃደ ሀገራዊ የጸጥታ መዋቅር ለመገንባት ያለመ መሆኑን ቢገልጽም፣ በተለይም በአማራ ክልል ከፍተኛ ፖለቲካዊ ተቃውሞን እና ቀጣይነት ያለውን ግጭት አስከትሏል። ይህ የሚያሳየው፣ የክልል መንግስታት የጸጥታ ተቋሞቻቸውን እንደ ህገ-መንግስታዊ የራስ ገዝ አስተዳደር መገለጫ አድርገው በሚያዩበት ፌደራላዊ ስርዓት ውስጥ፣ ኃይልን ማዕከላዊ ለማድረግ የሚደረግ ማንኛውም ሙከራ እንደ ፖለቲካዊ ጣልቃ ገብነት እንደሚቆጠር ነው።
መዋቅራዊ መፍትሄዎች፡ ኃይልን ብቻ ሳይሆን ህጉን ማስተካከል
የኢትዮጵያን ተደጋጋሚ የጸጥታ ቀውሶች በዘላቂነት ለመፍታት የተለያዩ መዋቅራዊ ማሻሻያዎችን ማድረግ የግድ ይላል። በቅድሚያ በአንቀጽ 51 እና በአንቀጽ 52 መካከል ያለውን የፌደራል እና የክልል የጸጥታ ኃላፊነቶች ግንኙነት በግልጽ በማብራራት የፌደራል መንግስት በምን ዓይነት ሁኔታዎች ውስጥ ጣልቃ መግባት እንዳለበት ህጋዊ ድንበር ሊቀመጥ ይገባል። በተጨማሪም የክልልን ራስን በራስ የማስተዳደር መብት በማይጋፋ መልኩ፣ መረጃ የሚለዋወጡበት እና ግጭቶች ወደ ጦርነት ከማምራታቸው በፊት የሚፈቱበት ቋሚ የፌደራል እና የክልል የጸጥታ ማስተባበሪያ መዋቅር መገንባት ያስፈልጋል።
በሌላ በኩል የፖሊስ ተቋማት ከፖለቲካ ወገንተኝነት የጸዱ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ እና በፖለቲካ የተነሳሱ የጸጥታ ጥሰቶችን የሚመረምር ገለልተኛ የቁጥጥር አካል በማቋቋም ተቋማዊ ተጠያቂነትን ማረጋገጥ ወሳኝ እርምጃ ነው። እንዲሁም የክልል ፖሊሶች ለክልል ፖለቲካዊ ፍላጎቶች ሳይሆን ለህገ-መንግስቱ እና ለህግ የበላይነት ታማኝ የሚሆኑበትን የጋራ ስልጠና እና ኦፕሬሽናል መርሆች በመተግበር የጋራ ፕሮፌሽናል አስተምህሮ ማዳበር ይገባል።
የኢትዮጵያ ተደጋጋሚ የጸጥታ ቀውሶች የሚያሳዩት "ህገ-መንግስታዊ ንድፍ ልክ እንደ ፖለቲካዊ አመራር ሁሉ እጅግ ወሳኝ መሆኑን" ነው። ዘላቂ ሰላም ጊዜያዊ ተኩስ አቁምን ወይም ወቅታዊ የጸጥታ ዘመቻዎችን ብቻ ተመርኩዞ ሊመጣ አይችልም። የኢትዮጵያ ማዕከላዊ ጥያቄ የጸጥታ ማሻሻያ ያስፈልጋል ወይ የሚለው ሳይሆን፣ ማሻሻያው የችግሩን ውጫዊ ምልክቶች ብቻ ሳይሆን ተቋማዊ እና ህገ-መንግስታዊ ስር-መሰረቱን ይፈታል ወይ የሚለው ነው።
Sponsored by
Surafel
8 days ago
ሳዳም በስቅላት!
በኢራቅ ጅምላ ጨራሽ መሳሪያዎች አልተገኙም!
#ethiopia | እ.ኤ.አ. መጋቢት 20 ቀን 2003 አሜሪካ ከብሪታንያ እና ከሌሎች አጋሮቿ ጋር በመሆን በኢራቅ ላይ ድንገተኛ ወረራ ፈጸመች።
የወረራው ዋነኛ ምክንያት ሳዳም ሁሴን የጅምላ ጨራሽ መሣሪያዎች ባለቤት ናቸው ለዓለምም ስጋት ደቅነዋል የሚል ነበረ።
ይህንን ተከትሎ በባግዳድ ሰማይ ስር የተካሄደው ከባድ የቦምብ ድብደባ የብዙ ንጹሃንን ሕይወት የቀጠፈ ሲሆን መኖሪያ ቤቶች፣ ሆስፒታሎች፣ ትምህርት ቤቶች እና መሠረተ ልማቶች እንዲወድሙ ምክንያት ሆኗል።
በርካታ ቤተሰቦች ሲፈናቀሉ፣ ሕፃናት ተቀብረዋል አገሪቱም እስከዛሬ ድረስ ወደማያበቃ መከራና ውዥንብር ውስጥ ገብታለች።
ከወራት መሸሸግ በኋላ በታህሳስ 13 ቀን 2003 ሳዳም ሁሴን በተክሪት አቅራቢያ በአሜሪካ ጦር ከተያዙ በኋላ በጥቅምት 19 ቀን 2005 በባግዳድ በከፍተኛ ጥበቃ ሥር በሚገኘው የኢራቅ ከፍተኛ ችሎት ፍርድ ቤት ቀረቡ።
በሕዳር 5 ቀን 2006 በ1982 በዱጃይል ከተፈጸመው የሰዎች ግድያ ጋር ተያይዞ በሰብአዊነት ላይ በተፈጸመ ወንጀል ጥፋተኛ ተብለው በሞት እንዲቀጡ የተወሰነባቸው ሲሆን፣ በታህሳስ 30 ቀን 2006 ቅጣታቸው ስቅላት ሆኗል።
ሆኖም ለወረራውና ለተከተለው የሃያ ዓመታት መከራ መነሻ የተደረጉት የጅምላ ጨራሽ መሣሪያዎች በኢራቅ ምድር በጭራሽ ሳይገኙ ቀርተዋል።
በያፌት ገ/ህይወት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
በኢራቅ ጅምላ ጨራሽ መሳሪያዎች አልተገኙም!
#ethiopia | እ.ኤ.አ. መጋቢት 20 ቀን 2003 አሜሪካ ከብሪታንያ እና ከሌሎች አጋሮቿ ጋር በመሆን በኢራቅ ላይ ድንገተኛ ወረራ ፈጸመች።
የወረራው ዋነኛ ምክንያት ሳዳም ሁሴን የጅምላ ጨራሽ መሣሪያዎች ባለቤት ናቸው ለዓለምም ስጋት ደቅነዋል የሚል ነበረ።
ይህንን ተከትሎ በባግዳድ ሰማይ ስር የተካሄደው ከባድ የቦምብ ድብደባ የብዙ ንጹሃንን ሕይወት የቀጠፈ ሲሆን መኖሪያ ቤቶች፣ ሆስፒታሎች፣ ትምህርት ቤቶች እና መሠረተ ልማቶች እንዲወድሙ ምክንያት ሆኗል።
በርካታ ቤተሰቦች ሲፈናቀሉ፣ ሕፃናት ተቀብረዋል አገሪቱም እስከዛሬ ድረስ ወደማያበቃ መከራና ውዥንብር ውስጥ ገብታለች።
ከወራት መሸሸግ በኋላ በታህሳስ 13 ቀን 2003 ሳዳም ሁሴን በተክሪት አቅራቢያ በአሜሪካ ጦር ከተያዙ በኋላ በጥቅምት 19 ቀን 2005 በባግዳድ በከፍተኛ ጥበቃ ሥር በሚገኘው የኢራቅ ከፍተኛ ችሎት ፍርድ ቤት ቀረቡ።
በሕዳር 5 ቀን 2006 በ1982 በዱጃይል ከተፈጸመው የሰዎች ግድያ ጋር ተያይዞ በሰብአዊነት ላይ በተፈጸመ ወንጀል ጥፋተኛ ተብለው በሞት እንዲቀጡ የተወሰነባቸው ሲሆን፣ በታህሳስ 30 ቀን 2006 ቅጣታቸው ስቅላት ሆኗል።
ሆኖም ለወረራውና ለተከተለው የሃያ ዓመታት መከራ መነሻ የተደረጉት የጅምላ ጨራሽ መሣሪያዎች በኢራቅ ምድር በጭራሽ ሳይገኙ ቀርተዋል።
በያፌት ገ/ህይወት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
8 days ago
የሀገርን ዕጣ ፈንታ ከፖለቲካ ልሂቃን እጅ ፈልቅቆ ለዜጎች ያስረከበው ሀገራዊ ምክክክር
*********************
በኢትዮጵያ የፖለቲካ ታሪክ ውስጥ አንዱ የኅብረተሰብ ክፍል እንደ ወርቃማ የታሪክ ዘመን የሚያየውን፣ ሌላው እንደ ጭቆና እና መገለል ዘመን ሲመለከተው መኖሩ የተለመደ ክስተት ሆኖ ቆይቷል።
ይህ የተራራቀ የታሪክ ግንዛቤ እና ያልተፈቱ መዋቅራዊ ቅራኔዎች ሀገራችንን ከትውልድ ወደ ትውልድ ለሚሸጋገር የትርክት ግጭት ዳርገዋታል።
ዘውዳዊውን ሥርዓት ተክቶ የመጣው ወታደራዊ አገዛዝም ሆነ፣ እርሱን ተከትሎ የመጣው የኢሕአዴግ ሥርዓት የዜጎችን የዴሞክራሲ፣ የፍትህ እና የእኩልነት ጥያቄዎች በዘላቂነት መፍታት አልቻሉም።
በተለይም ላለፉት ሦስት አሥርት ዓመታት የተዘረጋው የልዩነት ፖለቲካ፣ በዜጎች መካከል መጠራጠርን በማንገሥ የጋራ ሀገራዊ ማንነታችንን በጽኑ ፈትኖታል።
የ2010 ዓ.ም ሀገራዊ ለውጥ የፈጠረው የፖለቲካ መነቃቃት ትልቅ ተስፋን ያሰነቀ ቢሆንም፣ ከዴሞክራሲያዊ ባህል ማነስ እና ከጽንፈኛ ብሔርተኝነት ጋር ተዳምሮ አዳዲስ ሀገራዊ ስጋቶችን መፍጠሩ አልቀረም።
ይሁንና ከእነዚህ ሁሉ ውጣ ውረዶች ኢትዮጵያውያን አንድ ትልቅ ትምህርት ቀስመዋል። ይኸውም ታሪካዊ እና መዋቅራዊ ቀውሶችን በጦርነት፣ በኃይል እና በአሸናፊነት ሥነ-ልቦና ለመፍታት የሚደረግ ማንኛውም ሙከራ ጊዜያዊ ማስታገሻ እንጂ ዘላቂ መፍትሔ እንደማያመጣ ነው።
እውነተኛው መፍትሔ ያለው ጠብመንጃን አስቀምጦ በጠረጴዛ ዙሪያ በመቀመጥ፣ በመደማመጥ እና በሀሳብ ልዕልና በማመን ላይ ብቻ መሆኑ ታምኖበታል።
ይህን ታሪካዊ የዕይታ ሽግግር እውን ለማድረግ ነው የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በአዋጅ ቁጥር 1265/2014 ተቋቁሞ ወደ ሥራ የገባው። ከተቋሙ አወቃቀር ጀምሮ ሂደቱ ፍፁም የተለየ ነበር።
ከመነሻው፣ ከ632 እጩዎች ውስጥ በሕዝብ ተሳትፎ የተመረጡ 11 ኮሚሽነሮች ገለልተኛ ሆነው ኃላፊነቱን እንዲወስዱ ተደርጓል።
ይህ እርምጃ የፖለቲካ ልሂቃን ብቻ የሀገርን ዕጣ ፈንታ ሲዘውሩበት የነበረውን ባህል በመስበር፣ መሠረታዊው ዜጋ የሀገሩን ዕጣ ፈንታ በራሱ እንዲወስን ዕድል የፈጠረ አዲስ የፖለቲካ ምዕራፍ ነው።
የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ባለፉት ሁለት ዓመታት ከ1 ሺህ 200 በላይ ወረዳዎችን በማዳረስ ያከናወነው የአጀንዳ ማሰባሰብ ሥራ በኢትዮጵያ ታሪክ ታይቶ የማይታወቅ የዜጎች ተሳትፎ የተረጋገጠበት ነው።
ሴቶች፣ ወጣቶች፣ አርሶ አደሮች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አካል ጉዳተኞች፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ ተፈናቃዮች እንዲሁም ታጥቀው የሚንቀሳቀሱ አካላት እና የዳያስፖራው ማኅበረሰብ ሳይቀሩ በምክክሩ እንዲሳተፉ መደረጉ የሂደቱን አካታችነት እና ህዝባዊ መሠረት ያጎላዋል።
በአሁኑ ወቅት በመዲናችን አዲስ አበባ እየተካሄደ ያለው የሀገራዊ ምክክር ጉባኤ የዚህ ሁነኛ ማሳያ ነው።
ከ4 ሺህ በላይ በሕዝብ የተመረጡ ተወካዮች በራሳቸው ባህልና ቋንቋ፣ በነፃነት ስጋታቸውን እና ምኞታቸውን እያንፀባረቁበት ይገኛሉ።
ይህ ጉባኤ ስብሰባ ብቻ ሳይሆን፣ የተዛባውን የሀገራችንን ትርክት አርሞ፣ የተበታተነውን ሰፍቶ አንድ ላይ የሚያያይዝ የትውልዶች ድልድይ ነው።
መላ ኢትዮጵያውያን የራሳቸውን ችግር በራሳቸው አቅም፣ በሰከነ እና ዴሞክራሲያዊ በሆነ የምክክር ባህል ለመፍታት ያሳዩት ይህ ቁርጠኝነት ጠንካራ መሠረት ያለን ሀገረ-መንግሥት እንድንሆን ያስችለናል።
ጉባኤው የሚያቀርባቸው የፖሊሲ አማራጮች እና የሚያስቀምጣቸው የመፍትሔ አቅጣጫዎች፣ ለቀጣናው ሰላም ብቻ ሳይሆን በውስብስብ የፖለቲካ ቀውስ ውስጥ ለሚገኙ የዓለም ሀገራት ጭምር ትልቅ ተምሳሌት እንደሚሆኑ ይጠበቃል።
በሰለሞን ገዳ
#ethiopia #nationaldialogue #nationalconsensus #peacebuilding #ebc
*********************
በኢትዮጵያ የፖለቲካ ታሪክ ውስጥ አንዱ የኅብረተሰብ ክፍል እንደ ወርቃማ የታሪክ ዘመን የሚያየውን፣ ሌላው እንደ ጭቆና እና መገለል ዘመን ሲመለከተው መኖሩ የተለመደ ክስተት ሆኖ ቆይቷል።
ይህ የተራራቀ የታሪክ ግንዛቤ እና ያልተፈቱ መዋቅራዊ ቅራኔዎች ሀገራችንን ከትውልድ ወደ ትውልድ ለሚሸጋገር የትርክት ግጭት ዳርገዋታል።
ዘውዳዊውን ሥርዓት ተክቶ የመጣው ወታደራዊ አገዛዝም ሆነ፣ እርሱን ተከትሎ የመጣው የኢሕአዴግ ሥርዓት የዜጎችን የዴሞክራሲ፣ የፍትህ እና የእኩልነት ጥያቄዎች በዘላቂነት መፍታት አልቻሉም።
በተለይም ላለፉት ሦስት አሥርት ዓመታት የተዘረጋው የልዩነት ፖለቲካ፣ በዜጎች መካከል መጠራጠርን በማንገሥ የጋራ ሀገራዊ ማንነታችንን በጽኑ ፈትኖታል።
የ2010 ዓ.ም ሀገራዊ ለውጥ የፈጠረው የፖለቲካ መነቃቃት ትልቅ ተስፋን ያሰነቀ ቢሆንም፣ ከዴሞክራሲያዊ ባህል ማነስ እና ከጽንፈኛ ብሔርተኝነት ጋር ተዳምሮ አዳዲስ ሀገራዊ ስጋቶችን መፍጠሩ አልቀረም።
ይሁንና ከእነዚህ ሁሉ ውጣ ውረዶች ኢትዮጵያውያን አንድ ትልቅ ትምህርት ቀስመዋል። ይኸውም ታሪካዊ እና መዋቅራዊ ቀውሶችን በጦርነት፣ በኃይል እና በአሸናፊነት ሥነ-ልቦና ለመፍታት የሚደረግ ማንኛውም ሙከራ ጊዜያዊ ማስታገሻ እንጂ ዘላቂ መፍትሔ እንደማያመጣ ነው።
እውነተኛው መፍትሔ ያለው ጠብመንጃን አስቀምጦ በጠረጴዛ ዙሪያ በመቀመጥ፣ በመደማመጥ እና በሀሳብ ልዕልና በማመን ላይ ብቻ መሆኑ ታምኖበታል።
ይህን ታሪካዊ የዕይታ ሽግግር እውን ለማድረግ ነው የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በአዋጅ ቁጥር 1265/2014 ተቋቁሞ ወደ ሥራ የገባው። ከተቋሙ አወቃቀር ጀምሮ ሂደቱ ፍፁም የተለየ ነበር።
ከመነሻው፣ ከ632 እጩዎች ውስጥ በሕዝብ ተሳትፎ የተመረጡ 11 ኮሚሽነሮች ገለልተኛ ሆነው ኃላፊነቱን እንዲወስዱ ተደርጓል።
ይህ እርምጃ የፖለቲካ ልሂቃን ብቻ የሀገርን ዕጣ ፈንታ ሲዘውሩበት የነበረውን ባህል በመስበር፣ መሠረታዊው ዜጋ የሀገሩን ዕጣ ፈንታ በራሱ እንዲወስን ዕድል የፈጠረ አዲስ የፖለቲካ ምዕራፍ ነው።
የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ባለፉት ሁለት ዓመታት ከ1 ሺህ 200 በላይ ወረዳዎችን በማዳረስ ያከናወነው የአጀንዳ ማሰባሰብ ሥራ በኢትዮጵያ ታሪክ ታይቶ የማይታወቅ የዜጎች ተሳትፎ የተረጋገጠበት ነው።
ሴቶች፣ ወጣቶች፣ አርሶ አደሮች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አካል ጉዳተኞች፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ ተፈናቃዮች እንዲሁም ታጥቀው የሚንቀሳቀሱ አካላት እና የዳያስፖራው ማኅበረሰብ ሳይቀሩ በምክክሩ እንዲሳተፉ መደረጉ የሂደቱን አካታችነት እና ህዝባዊ መሠረት ያጎላዋል።
በአሁኑ ወቅት በመዲናችን አዲስ አበባ እየተካሄደ ያለው የሀገራዊ ምክክር ጉባኤ የዚህ ሁነኛ ማሳያ ነው።
ከ4 ሺህ በላይ በሕዝብ የተመረጡ ተወካዮች በራሳቸው ባህልና ቋንቋ፣ በነፃነት ስጋታቸውን እና ምኞታቸውን እያንፀባረቁበት ይገኛሉ።
ይህ ጉባኤ ስብሰባ ብቻ ሳይሆን፣ የተዛባውን የሀገራችንን ትርክት አርሞ፣ የተበታተነውን ሰፍቶ አንድ ላይ የሚያያይዝ የትውልዶች ድልድይ ነው።
መላ ኢትዮጵያውያን የራሳቸውን ችግር በራሳቸው አቅም፣ በሰከነ እና ዴሞክራሲያዊ በሆነ የምክክር ባህል ለመፍታት ያሳዩት ይህ ቁርጠኝነት ጠንካራ መሠረት ያለን ሀገረ-መንግሥት እንድንሆን ያስችለናል።
ጉባኤው የሚያቀርባቸው የፖሊሲ አማራጮች እና የሚያስቀምጣቸው የመፍትሔ አቅጣጫዎች፣ ለቀጣናው ሰላም ብቻ ሳይሆን በውስብስብ የፖለቲካ ቀውስ ውስጥ ለሚገኙ የዓለም ሀገራት ጭምር ትልቅ ተምሳሌት እንደሚሆኑ ይጠበቃል።
በሰለሞን ገዳ
#ethiopia #nationaldialogue #nationalconsensus #peacebuilding #ebc
9 days ago
የእዝ እና የድርጅት አመራር የነበሩ 14 አባላት በሐገራዊ ምክክሩ እየተሳተፉ እንደሆነ ካፒቴን ማስረሻ ሰጤ ተናገሩ
የመንግስትን የሰላም ጥሪ በመቀበል ከትጥቅ ትግል ወደ ሰላማዊ የፖለቲካ መድረክ የተቀላቀሉት ካፒቴን ማስረሻ ሰጤ፣ የዕዝና የድርጅት አመራር የነበሩ 14 አባላት በውክልና ኮታ በሐገራዊ ምክክር መድረኩ እየተሳተፉ እንደሆነ ገልጸዋል።
ካፒቴን ማስረሻ ለአሐዱ ሬዲዮ እንደገለጹት፣ ታጣቂዎችን ወደ ጫካ ያስገቡት መሰረታዊ የፖለቲካ ጥያቄዎች አሁን ላይ በሃገራዊ ምክክር ጉባኤው እየተመከረባቸው ነው።
አመራሮቹ በአማራ ክልልም ሆነ በሌሎች የሀገሪቱ ክፍሎች የሚነሱ ለትጥቅ ትግል መነሻ የሆኑ ጥያቄዎች ለውይይት መቅረባቸውንም አንስተዋል።
"ከጫካ ትግል ተመልሰን፤ ጥያቄዎቻችንን ከሌላው ኢትዮጵያዊ ጋር በጋራ ለመፍታት ለምክክር ተቀምጠናል" ያሉት ካፒቴን ማስረሻ፣ አንገብጋቢ የሚሏቸውን ጉዳዮች በአጀንዳ ማሰባሰብ ወቅት ለኮሚሽኑ ማስረከባቸውን አስታውሰዋል።
አሁን ላይ በምክክር መድረኩ እየተመከረባቸው ያሉት 8 አጀንዳዎች ተስፋ ሰጪ መሆናቸውን ገልጸው፣ የሀገር ግንባታ እና የመንግስት አወቃቀርን የተመለከቱ ጉዳዮች እልባት የሚፈልጋቸው አንኳር ጥያቄዎች ናቸው ብለው እንደሚያምኑ ተናግረዋል።
ካፒቴን ማስረሻ የምክክር መድረኩ ለዘመናት ሲንከባለሉ ለመጡ ፖለቲካዊ ችግሮች ዘላቂ መፍትሄ በማምጣት የተሻለ መንገድ ነው የሚል እምነት እንዳላቸው ገልጸዋል።
#አሐዱ
የመንግስትን የሰላም ጥሪ በመቀበል ከትጥቅ ትግል ወደ ሰላማዊ የፖለቲካ መድረክ የተቀላቀሉት ካፒቴን ማስረሻ ሰጤ፣ የዕዝና የድርጅት አመራር የነበሩ 14 አባላት በውክልና ኮታ በሐገራዊ ምክክር መድረኩ እየተሳተፉ እንደሆነ ገልጸዋል።
ካፒቴን ማስረሻ ለአሐዱ ሬዲዮ እንደገለጹት፣ ታጣቂዎችን ወደ ጫካ ያስገቡት መሰረታዊ የፖለቲካ ጥያቄዎች አሁን ላይ በሃገራዊ ምክክር ጉባኤው እየተመከረባቸው ነው።
አመራሮቹ በአማራ ክልልም ሆነ በሌሎች የሀገሪቱ ክፍሎች የሚነሱ ለትጥቅ ትግል መነሻ የሆኑ ጥያቄዎች ለውይይት መቅረባቸውንም አንስተዋል።
"ከጫካ ትግል ተመልሰን፤ ጥያቄዎቻችንን ከሌላው ኢትዮጵያዊ ጋር በጋራ ለመፍታት ለምክክር ተቀምጠናል" ያሉት ካፒቴን ማስረሻ፣ አንገብጋቢ የሚሏቸውን ጉዳዮች በአጀንዳ ማሰባሰብ ወቅት ለኮሚሽኑ ማስረከባቸውን አስታውሰዋል።
አሁን ላይ በምክክር መድረኩ እየተመከረባቸው ያሉት 8 አጀንዳዎች ተስፋ ሰጪ መሆናቸውን ገልጸው፣ የሀገር ግንባታ እና የመንግስት አወቃቀርን የተመለከቱ ጉዳዮች እልባት የሚፈልጋቸው አንኳር ጥያቄዎች ናቸው ብለው እንደሚያምኑ ተናግረዋል።
ካፒቴን ማስረሻ የምክክር መድረኩ ለዘመናት ሲንከባለሉ ለመጡ ፖለቲካዊ ችግሮች ዘላቂ መፍትሄ በማምጣት የተሻለ መንገድ ነው የሚል እምነት እንዳላቸው ገልጸዋል።
#አሐዱ
9 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) በኢትዮጵያ ከሚገኙ አንጋፋ የግል ባንኮች አንዱ የሆነው አቢሲኒያ ባንክ የኢትዮጵያ ሰነደ ሙዓለ ንዋይ ገበያን (ESX) በመቀላቀል አምስተኛው ባንክ ሆኗል። ይህ እርምጃ ሀገሪቱ እያሳደገችው ላለው የካፒታል ገበያ መስፋፋት ትልቅ ምዕራፍ ተብሏል።
ባንኩ ዛሬጁላይ 28, 2026 በንግድ ትምህርት ቤት አካባቢ በሚገኘው የገበያው ዋና መስሪያ ቤት በተካሄደ የደወል መደወል ሥነ-ሥርዓት ወደ ሁለተኛ ደረጃ ገበያው በይፋ ገብቷል። ባንኩ 15 ሚሊዮን ነባር መደበኛ አክሲዮኖችን ለገበያ ያቀረበ ሲሆን፣ በተጨማሪም 3.125 ሚሊዮን አዳዲስ መደበኛ አክሲዮኖችን እያንዳንዳቸውን በ1,600 ብር መነሻ ዋጋ አቅርቧል። በዚህም በገበያው ላይ የገቡት አጠቃላይ የባንኩ የተፈቀዱ አክሲዮኖች ብዛት 17,481,120 ደርሷል።
የገበያውን መከፈት ተከትሎ በተደረገው የዛሬው የግብይት ውሎ፣ የባንኩ የአክሲዮን ዋጋ በከፍተኛ ሁኔታ ማሻቀቡ ታይቷል። ከ2,594 ያላነሱ አክሲዮኖች በአማካይ በ2,000 ብር የተሸጡ ሲሆን፣ ወደ 1,000 የሚጠጉ አክሲዮኖች ደግሞ መነሻ ዋጋውን በእጥፍ ገደማ በማሳደግ እስከ 3,000 ብር በሚደርስ ዋጋ ተገበያይተዋል። ይህ ምዝገባ ነባር ባለአክሲዮኖች ድርሻቸውን በተደራጀ የግብይት መድረክ ላይ እንዲሸጡ ከማስቻሉም በላይ፣ አዳዲስ አክሲዮኖችን በማቅረብ ለባንኩ ትልቅ ካፒታል ያሰባስባል።
ከኢትዮ ቴሌኮም በመቀጠል በካፒታል ገበያው ላይ የተመዘገበው ስድስተኛው ተቋም የሆነው አቢሲኒያ ባንክ፣ እ.ኤ.አ. በየካቲት 1996 በ131 መስራች ባለአክሲዮኖች በ17.8 ሚሊዮን ብር የተከፈለ ካፒታል ነበር የተቋቋመው። በደወል መደወል ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የተገኙት የባንኩ ፕሬዚዳንት አቶ በቃሉ ዘለቀ፣ ይህ ምዝገባ በባንኩ ታሪክ አዲስ ምዕራፍ የከፈተ እና ታሪካዊ ክስተት መሆኑን ተናግረዋል።
የኢትዮጵያ ሰነደ ሙዓለ ንዋይ ገበያ ዋና ስራ አስፈፃሚ ዶ/ር ጥላሁን እስማኤል የባንኩን ውሳኔ አድንቀው፣ እያንዳንዱ አዲስ ምዝገባ የኢትዮጵያን የካፒታል ገበያ መሰረት እንደሚያጠናክር ገልጸዋል። አክለውም፣ የአቢሲኒያ ባንክ በገበያው ውስጥ መመዝገብ በሀገሪቱ የገበያ ተቋማት ላይ ያለውን እምነት የሚያንጸባርቅ እና አንጋፋ የኢትዮጵያ ኩባንያዎች ከፍተኛውን የአስተዳደር፣ የግልጽነት እና የባለሀብቶች ተሳትፎ ደረጃን እየተቀበሉ መሆናቸውን በተግባር የሚያሳይ ነው ሲሉ የባንኩን እርምጃ አብራርተዋል።
ባንኩ ዛሬጁላይ 28, 2026 በንግድ ትምህርት ቤት አካባቢ በሚገኘው የገበያው ዋና መስሪያ ቤት በተካሄደ የደወል መደወል ሥነ-ሥርዓት ወደ ሁለተኛ ደረጃ ገበያው በይፋ ገብቷል። ባንኩ 15 ሚሊዮን ነባር መደበኛ አክሲዮኖችን ለገበያ ያቀረበ ሲሆን፣ በተጨማሪም 3.125 ሚሊዮን አዳዲስ መደበኛ አክሲዮኖችን እያንዳንዳቸውን በ1,600 ብር መነሻ ዋጋ አቅርቧል። በዚህም በገበያው ላይ የገቡት አጠቃላይ የባንኩ የተፈቀዱ አክሲዮኖች ብዛት 17,481,120 ደርሷል።
የገበያውን መከፈት ተከትሎ በተደረገው የዛሬው የግብይት ውሎ፣ የባንኩ የአክሲዮን ዋጋ በከፍተኛ ሁኔታ ማሻቀቡ ታይቷል። ከ2,594 ያላነሱ አክሲዮኖች በአማካይ በ2,000 ብር የተሸጡ ሲሆን፣ ወደ 1,000 የሚጠጉ አክሲዮኖች ደግሞ መነሻ ዋጋውን በእጥፍ ገደማ በማሳደግ እስከ 3,000 ብር በሚደርስ ዋጋ ተገበያይተዋል። ይህ ምዝገባ ነባር ባለአክሲዮኖች ድርሻቸውን በተደራጀ የግብይት መድረክ ላይ እንዲሸጡ ከማስቻሉም በላይ፣ አዳዲስ አክሲዮኖችን በማቅረብ ለባንኩ ትልቅ ካፒታል ያሰባስባል።
ከኢትዮ ቴሌኮም በመቀጠል በካፒታል ገበያው ላይ የተመዘገበው ስድስተኛው ተቋም የሆነው አቢሲኒያ ባንክ፣ እ.ኤ.አ. በየካቲት 1996 በ131 መስራች ባለአክሲዮኖች በ17.8 ሚሊዮን ብር የተከፈለ ካፒታል ነበር የተቋቋመው። በደወል መደወል ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የተገኙት የባንኩ ፕሬዚዳንት አቶ በቃሉ ዘለቀ፣ ይህ ምዝገባ በባንኩ ታሪክ አዲስ ምዕራፍ የከፈተ እና ታሪካዊ ክስተት መሆኑን ተናግረዋል።
የኢትዮጵያ ሰነደ ሙዓለ ንዋይ ገበያ ዋና ስራ አስፈፃሚ ዶ/ር ጥላሁን እስማኤል የባንኩን ውሳኔ አድንቀው፣ እያንዳንዱ አዲስ ምዝገባ የኢትዮጵያን የካፒታል ገበያ መሰረት እንደሚያጠናክር ገልጸዋል። አክለውም፣ የአቢሲኒያ ባንክ በገበያው ውስጥ መመዝገብ በሀገሪቱ የገበያ ተቋማት ላይ ያለውን እምነት የሚያንጸባርቅ እና አንጋፋ የኢትዮጵያ ኩባንያዎች ከፍተኛውን የአስተዳደር፣ የግልጽነት እና የባለሀብቶች ተሳትፎ ደረጃን እየተቀበሉ መሆናቸውን በተግባር የሚያሳይ ነው ሲሉ የባንኩን እርምጃ አብራርተዋል።
Sponsored by
Surafel
9 days ago
የምክክር ኮሚሽኑ የአራት ዓመታት ጉዞ እና የሀገራዊ ምክክር ጉባኤው አዲስ ምዕራፍ
*********************
ኢትዮጵያ ለዘመናት የዘለቁ ውስብስብ ሀገራዊ ልዩነቶችንና ቅሬታዎችን በሰለጠነ መንገድ፣ በውይይትና በምክክር ለመፍታት ያደረገችው ጥረት ታሪካዊ ምዕራፍ ላይ ደርሷል።
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከተቋቋመበት ጊዜ ጀምሮ ባለፉት አራት ዓመታት በርካታ ፈታኝና መሠረታዊ የዝግጅት ሥራዎችን ሲያከናውን የቆየ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት ደግሞ የጠቅላላው ሂደት ማጠቃለያ ወደሆነው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ተሸጋግሯል።
ኮሚሽኑ የተጣለበትን ታሪካዊ ኃላፊነት ለመወጣት ባለፉት ዓመታት ትኩረት ሰጥቶ የሠራቸው ዐበይት ተግባራት በሚከተሉት ዋና ዋና ዘርፎች የሚከፈሉ ናቸው።
✅ የተቋም ግንባታና የህግ ማዕቀፍ ዝግጅት
ኮሚሽኑ ሥራውን በግልጽነትና በተጠያቂነት መምራት የሚያስችሉ መመሪያዎችን፣ የሥነ-ምግባር ደንቦችንና የአሠራር ሥርዓቶችን ዘርግቷል። ነፃነቱንና ገለልተኝነቱን በጠበቀ መልኩ የተዋቀረው ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን፣ የኅብረተሰቡን እምነት ለመገንባት የሚያስችሉ በርካታ የማንቃትና የማስተዋወቅ ሥራዎችን አከናውኗል።
✅ የባለድርሻ አካላት እና የቁልፍ ተሳታፊዎች ልየታ
የምክክር ሂደቱ ሁሉንም አሳታፊ (Inclusive) ለማድረግ በሁሉም የሀገራችን ክልሎች እና የከተማ አስተዳደሮች እስከ ወረዳና ቀበሌ ድረስ የወረዱ የባለድርሻ አካላት ልየታዎች ተካሂደዋል።
በሂደቱም የተለያዩ የኅብረተሰብ ክፍሎች ወጣቶች፣ ሴቶች፣ የእድሜ ባለጸጎች፣ አካል ጉዳተኞች፣ ነጋዴዎች፣ የፖለቲካ ፓርቲዎችና የሲቪክ ማህበራት፣ የሃይማኖት አባቶችና የሀገር ሽማግሌዎች፣ የመንግሥት አካላትና የጸጥታ ተቋማት ተወካዮች እንዲሳተፉ ተደርጓል።
✅ የአጀንዳ ማሰባሰብ ሂደት
የምክክር ሂደቱ እውነተኛ የሕዝብ ድምፅ እንዲሆን በክልሎችና በከተማ አስተዳደሮች ደረጃ ሰፊ የአጀንዳ ማሰባሰብ መድረኮች ተካሂደዋል።
በእነዚህ መድረኮች ኅብረተሰቡ ለሀገራዊ አንድነት፣ ለሰላም፣ ለፍትህና ለሕገ-መንግሥታዊ ጉዳዮች መፍትሔ ይሆናሉ ያላቸውን ሐሳቦችና ቅሬታዎች በነፃነት እንዲያቀርብ ተደርጓል።
✅ የአጀንዳዎች ውህደትና ማዋቀር
ከመላው የሀገራችን አካባቢዎች የተሰበሰቡ የተለያዩ አጀንዳዎች በባለሙያዎችና በኮሚሽነሮች አማካኝነት በጥራት ተደራጅተው፣ ተመሳሳይነታቸው ተለይቶ እና ተዋቅረው ለሀገራዊ ምክክር ጉባኤው እንዲቀርቡ ተደርገዋል።
✅ አሁን ላይ ያለው የሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ምዕራፍ
ባለፉት አራት ዓመታት የተሠሩት መሠረታዊ ሥራዎች ውጤት የሆነው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ፣ አሁን ላይ ትልቁ የትኩረት ማዕከል ሆኗል። ይህ ጉባኤ ከየአካባቢው የተወከሉ ከ4 ሺህ በላይ ተመካካሪዎች እና ቁልፍ ባለድርሻ አካላት በአንድ ጠረጴዛ ዙሪያ ተቀምጠው ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ በስፋት የሚመክሩበት ታሪካዊ መድረክ ነው።
✅ የጉባኤው ዋና ዋና ትኩረቶችና ግቦች
1.በአጀንዳዎች ላይ በጥልቀት መምከር፡- ከመነሻው ጀምሮ ከተሰበሰቡት አጀንዳዎች መካከል ዋና ዋና ሀገራዊ መግባባት በሚያስፈልጋቸው ጉዳዮች ለአብነት ያህል ሕገ-መንግሥታዊ ማሻሻያዎች፣ የሀገረ-መንግሥት ግንባታ፣ የታሪክ ትርክት፣ የሰላምና ደኅንነት ሥርዓት ላይ ነፃና ግልጽ ውይይት ማድረግ።
2. የተሰበሰቡ ሐሳቦችን ማደራጀትና ማቀራረብ፡- ኮሚሽኑ ከታች ጀምሮ ያሰባሰባቸውን አጀንዳዎች ላ በጥልቀት በመምከር በሀገራዊ ፍላጎቶችና የጋራ እሴቶች ላይ ያተኮረ መግባባት መፍጠር።
3. የመፍትሔ ሐሳቦችና የውሳኔ አስተያየቶች ማዘጋጀት፡- በምክክር ጉባኤው በሚደረጉ ውይይቶች መሠረት ለሀገራዊ ችግሮች ዘላቂ መፍትሔ የሚሆኑ የፖሊሲ፣ የሕግና የተቋማት ማሻሻያ ሐሳቦችን አዘጋጅቶ ለሚመለከታቸው የመንግሥት አካላትና ለሕዝብ ማቅረብ ናቸው።
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ባለፉት አራት ዓመታት የተጓዘበት መንገድ በፈተናዎች እና በተስፋዎች የተሞላ ቢሆንም፣ በሀገራችን በረጅም ታሪክ ውስጥ የመጀመሪያው በሆነው በዚህ አሳታፊ ሂደት፣ ከቀበሌ እስከ ሀገር አቀፍ ደረጃ የተካሄዱት እንቅስቃሴዎች የሕዝብን ድምፅ የመስማት ትልቅ መሠረት ጥለዋል።
አሁን ላይ እየተካሄደ ያለው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ደግሞ፣ የዚሁ ሁሉ ድካም ፍሬ የሚታይበት፣ የኢትዮጵያን የወደፊት የፖለቲካና የማኅበራዊ መስመር የሚቀርጽ በመሆኑ የሁሉም ዜጎች፣ የፖለቲካ ኃይሎች እና ባለድርሻ አካላት በጎ ፈቃድና ንቁ ተሳትፎ ወሳኝ ነው።
በአድማሱ አራጋው
#ethiopianbroadcastingcorporation #nationaldialogue #ethiopiannationaldialogue #inclusivedialogue
*********************
ኢትዮጵያ ለዘመናት የዘለቁ ውስብስብ ሀገራዊ ልዩነቶችንና ቅሬታዎችን በሰለጠነ መንገድ፣ በውይይትና በምክክር ለመፍታት ያደረገችው ጥረት ታሪካዊ ምዕራፍ ላይ ደርሷል።
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከተቋቋመበት ጊዜ ጀምሮ ባለፉት አራት ዓመታት በርካታ ፈታኝና መሠረታዊ የዝግጅት ሥራዎችን ሲያከናውን የቆየ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት ደግሞ የጠቅላላው ሂደት ማጠቃለያ ወደሆነው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ተሸጋግሯል።
ኮሚሽኑ የተጣለበትን ታሪካዊ ኃላፊነት ለመወጣት ባለፉት ዓመታት ትኩረት ሰጥቶ የሠራቸው ዐበይት ተግባራት በሚከተሉት ዋና ዋና ዘርፎች የሚከፈሉ ናቸው።
✅ የተቋም ግንባታና የህግ ማዕቀፍ ዝግጅት
ኮሚሽኑ ሥራውን በግልጽነትና በተጠያቂነት መምራት የሚያስችሉ መመሪያዎችን፣ የሥነ-ምግባር ደንቦችንና የአሠራር ሥርዓቶችን ዘርግቷል። ነፃነቱንና ገለልተኝነቱን በጠበቀ መልኩ የተዋቀረው ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን፣ የኅብረተሰቡን እምነት ለመገንባት የሚያስችሉ በርካታ የማንቃትና የማስተዋወቅ ሥራዎችን አከናውኗል።
✅ የባለድርሻ አካላት እና የቁልፍ ተሳታፊዎች ልየታ
የምክክር ሂደቱ ሁሉንም አሳታፊ (Inclusive) ለማድረግ በሁሉም የሀገራችን ክልሎች እና የከተማ አስተዳደሮች እስከ ወረዳና ቀበሌ ድረስ የወረዱ የባለድርሻ አካላት ልየታዎች ተካሂደዋል።
በሂደቱም የተለያዩ የኅብረተሰብ ክፍሎች ወጣቶች፣ ሴቶች፣ የእድሜ ባለጸጎች፣ አካል ጉዳተኞች፣ ነጋዴዎች፣ የፖለቲካ ፓርቲዎችና የሲቪክ ማህበራት፣ የሃይማኖት አባቶችና የሀገር ሽማግሌዎች፣ የመንግሥት አካላትና የጸጥታ ተቋማት ተወካዮች እንዲሳተፉ ተደርጓል።
✅ የአጀንዳ ማሰባሰብ ሂደት
የምክክር ሂደቱ እውነተኛ የሕዝብ ድምፅ እንዲሆን በክልሎችና በከተማ አስተዳደሮች ደረጃ ሰፊ የአጀንዳ ማሰባሰብ መድረኮች ተካሂደዋል።
በእነዚህ መድረኮች ኅብረተሰቡ ለሀገራዊ አንድነት፣ ለሰላም፣ ለፍትህና ለሕገ-መንግሥታዊ ጉዳዮች መፍትሔ ይሆናሉ ያላቸውን ሐሳቦችና ቅሬታዎች በነፃነት እንዲያቀርብ ተደርጓል።
✅ የአጀንዳዎች ውህደትና ማዋቀር
ከመላው የሀገራችን አካባቢዎች የተሰበሰቡ የተለያዩ አጀንዳዎች በባለሙያዎችና በኮሚሽነሮች አማካኝነት በጥራት ተደራጅተው፣ ተመሳሳይነታቸው ተለይቶ እና ተዋቅረው ለሀገራዊ ምክክር ጉባኤው እንዲቀርቡ ተደርገዋል።
✅ አሁን ላይ ያለው የሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ምዕራፍ
ባለፉት አራት ዓመታት የተሠሩት መሠረታዊ ሥራዎች ውጤት የሆነው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ፣ አሁን ላይ ትልቁ የትኩረት ማዕከል ሆኗል። ይህ ጉባኤ ከየአካባቢው የተወከሉ ከ4 ሺህ በላይ ተመካካሪዎች እና ቁልፍ ባለድርሻ አካላት በአንድ ጠረጴዛ ዙሪያ ተቀምጠው ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ በስፋት የሚመክሩበት ታሪካዊ መድረክ ነው።
✅ የጉባኤው ዋና ዋና ትኩረቶችና ግቦች
1.በአጀንዳዎች ላይ በጥልቀት መምከር፡- ከመነሻው ጀምሮ ከተሰበሰቡት አጀንዳዎች መካከል ዋና ዋና ሀገራዊ መግባባት በሚያስፈልጋቸው ጉዳዮች ለአብነት ያህል ሕገ-መንግሥታዊ ማሻሻያዎች፣ የሀገረ-መንግሥት ግንባታ፣ የታሪክ ትርክት፣ የሰላምና ደኅንነት ሥርዓት ላይ ነፃና ግልጽ ውይይት ማድረግ።
2. የተሰበሰቡ ሐሳቦችን ማደራጀትና ማቀራረብ፡- ኮሚሽኑ ከታች ጀምሮ ያሰባሰባቸውን አጀንዳዎች ላ በጥልቀት በመምከር በሀገራዊ ፍላጎቶችና የጋራ እሴቶች ላይ ያተኮረ መግባባት መፍጠር።
3. የመፍትሔ ሐሳቦችና የውሳኔ አስተያየቶች ማዘጋጀት፡- በምክክር ጉባኤው በሚደረጉ ውይይቶች መሠረት ለሀገራዊ ችግሮች ዘላቂ መፍትሔ የሚሆኑ የፖሊሲ፣ የሕግና የተቋማት ማሻሻያ ሐሳቦችን አዘጋጅቶ ለሚመለከታቸው የመንግሥት አካላትና ለሕዝብ ማቅረብ ናቸው።
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ባለፉት አራት ዓመታት የተጓዘበት መንገድ በፈተናዎች እና በተስፋዎች የተሞላ ቢሆንም፣ በሀገራችን በረጅም ታሪክ ውስጥ የመጀመሪያው በሆነው በዚህ አሳታፊ ሂደት፣ ከቀበሌ እስከ ሀገር አቀፍ ደረጃ የተካሄዱት እንቅስቃሴዎች የሕዝብን ድምፅ የመስማት ትልቅ መሠረት ጥለዋል።
አሁን ላይ እየተካሄደ ያለው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ደግሞ፣ የዚሁ ሁሉ ድካም ፍሬ የሚታይበት፣ የኢትዮጵያን የወደፊት የፖለቲካና የማኅበራዊ መስመር የሚቀርጽ በመሆኑ የሁሉም ዜጎች፣ የፖለቲካ ኃይሎች እና ባለድርሻ አካላት በጎ ፈቃድና ንቁ ተሳትፎ ወሳኝ ነው።
በአድማሱ አራጋው
#ethiopianbroadcastingcorporation #nationaldialogue #ethiopiannationaldialogue #inclusivedialogue
9 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) ዛሬ ማክሰኞ በደቡብ ምዕራብ ጃፓን ኪዩሹ ደሴት (በተለይም ኩማሞቶ ግዛት) በሬክተር ስኬል 7.1 የተመዘገበ ከባድ የመሬት መንቀጥቀጥ መከሰቱን ተከትሎ ሕንፃዎች ፈርሰዋል እንዲሁም ቃጠሎዎች ተነስተዋል። በካሺማ ከተማ በሚገኝ "ኢዮን ሞል" በተሰኘ የገበያ ማዕከል ሁለተኛ ፎቅ በመደርመሱ በርካታ ሰዎች ፍርስራሽ ስር ተጣብቀው የቀሩ ሲሆን፣ የበርካታ ሰዎች ሕይወት ማለፉን የፖሊስ ምንጮች ቢጠቁሙም ትክክለኛውን ቁጥር ለማረጋገጥ ጊዜ እንደሚወስድ ተገልጿል።
የጃፓን ጠቅላይ ሚኒስትር ሳናይ ታካይቺ አደጋውን አረጋግጠው የጉዳቱን መጠን እያጣሩ መሆኑን ተናግረዋል። የሀገሪቱ ብሔራዊ ቴሌቪዥን ቢያንስ 50 ሰዎች ወደ ሆስፒታል መወሰዳቸውን የዘገበ ሲሆን፣ ከሀዲድ የወጡ ባቡሮች፣ የፈረሱ ድልድዮች እና የተሰነጠቁ መንገዶች በምስል ታይተዋል። በመነሻው የሱናሚ ማስጠንቀቂያ ተሰጥቶ የነበረ ቢሆንም ከሰዓታት በኋላ ተነስቷል።
በአደጋው ምክንያት በኩማሞቶ ግዛት ወደ 45,000 የሚጠጉ አባወራዎች የመብራት አገልግሎት የተቋረጠባቸው ቢሆንም፣ በአካባቢው በሚገኙ የኒውክሌር ኃይል ማመንጫዎች ላይ ምንም ዓይነት የደህንነት ችግር እንዳልተመዘገበ ባለስልጣናት አረጋግጠዋል። ይኸው ኩማሞቶ ግዛት እ.ኤ.አ. በ2016 በደረሰ ድርብ የመሬት መንቀጥቀጥ የ273 ሰዎች ሕይወት ማለፉ የሚታወስ ነው።
የጃፓን ጠቅላይ ሚኒስትር ሳናይ ታካይቺ አደጋውን አረጋግጠው የጉዳቱን መጠን እያጣሩ መሆኑን ተናግረዋል። የሀገሪቱ ብሔራዊ ቴሌቪዥን ቢያንስ 50 ሰዎች ወደ ሆስፒታል መወሰዳቸውን የዘገበ ሲሆን፣ ከሀዲድ የወጡ ባቡሮች፣ የፈረሱ ድልድዮች እና የተሰነጠቁ መንገዶች በምስል ታይተዋል። በመነሻው የሱናሚ ማስጠንቀቂያ ተሰጥቶ የነበረ ቢሆንም ከሰዓታት በኋላ ተነስቷል።
በአደጋው ምክንያት በኩማሞቶ ግዛት ወደ 45,000 የሚጠጉ አባወራዎች የመብራት አገልግሎት የተቋረጠባቸው ቢሆንም፣ በአካባቢው በሚገኙ የኒውክሌር ኃይል ማመንጫዎች ላይ ምንም ዓይነት የደህንነት ችግር እንዳልተመዘገበ ባለስልጣናት አረጋግጠዋል። ይኸው ኩማሞቶ ግዛት እ.ኤ.አ. በ2016 በደረሰ ድርብ የመሬት መንቀጥቀጥ የ273 ሰዎች ሕይወት ማለፉ የሚታወስ ነው።
10 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የእስራኤል አየር ኃይል በዮርዳኖስ ድንበር አቅራቢያ አየር ላይ የነበረን አንድ ሰው አልባ አውሮፕላን ከጥቂት ደቂቃዎች በፊት መጥለፉንና መትቶ መጣሉን የእስራኤል መከላከያ ኃይል አስታወቀ።
መከላከያ ኃይሉ አክሎ እንዳብራራው ሰው አልባ አውሮፕላኗ ወደ እስራኤል ግዛት ጥሳ አልገባችም፤ በዚህም ምክንያት በአሰራር ደንቡ መሰረት ምንም ዓይነት የአደጋ ጊዜ ማስጠንቀቂያ (ሳይረን) አልተሰማም።
ይሁን እንጂ የድሮኗ መነሻ ከየት እንደሆነ እስካሁን በውል ያልታወቀ ሲሆን፣ ክስተቱ አሁንም በምርመራ ላይ እንደሚገኝ መከላከያ ኃይሉ አረጋግጧል።
መከላከያ ኃይሉ አክሎ እንዳብራራው ሰው አልባ አውሮፕላኗ ወደ እስራኤል ግዛት ጥሳ አልገባችም፤ በዚህም ምክንያት በአሰራር ደንቡ መሰረት ምንም ዓይነት የአደጋ ጊዜ ማስጠንቀቂያ (ሳይረን) አልተሰማም።
ይሁን እንጂ የድሮኗ መነሻ ከየት እንደሆነ እስካሁን በውል ያልታወቀ ሲሆን፣ ክስተቱ አሁንም በምርመራ ላይ እንደሚገኝ መከላከያ ኃይሉ አረጋግጧል።
10 days ago
ለመጪው ትውልድ የተተከለ ተስፋ፤ የኢትዮጵያ አረንጓዴ ጉዞ
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 20፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ለብዙ ዓመታት ከፍተኛ የመሬት መሸርሸር ተደጋጋሚ ድርቅ እና የደን ሽፋን መሳሳት ለኢትዮጵያ ሥነ ምህዳራዊ ሚዛን እና የግብርና ምርታማነት ትልቅ አደጋ ደቅነው ቆይተዋል።
አሁን ግን የአረንጓዴ ልማትና የደን ሽፋን ንቅናቄ መልክዓ ምድርን እየለወጠ፤ በመላ ሀገሪቱ በተደረገ ስልታዊ አመራር ኢትዮጵያ የአካባቢ ጥበቃ ታሪኳን በአዲስ መልክ እየጻፈች ትገኛለች።
በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አነሳሽነት በተጀመረው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር እየተመራች ሀገሪቱ በዘመናዊ ታሪክ ውስጥ እጅግ ግዙፍ ከሆኑት ተፈጥሮ ተኮር መፍትሔዎች አንዱን እየተገበረች ትገኛለች::
ይህም በሚሊየን የሚቆጠር ሄክታር መሬት በማንሰራራት ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር አረንጓዴ ኢኮኖሚ መገንባት የሚያስችል ሲሆን ÷ ወደ አረንጓዴ መሪነት የሚያሸጋግረው የኢትዮጵያ የረጅም ጊዜ የአካባቢ ጥበቃ ግብ ግልጽ እና ለውጥ አምጪ ነው፡፡
እስከ ፈረንጆቹ 2030 ድረስ የሀገሪቱን የደን ሽፋን ወደ 30 በመቶ ማሳደግ እና ከ54 ሚሊየን ሄክታር በላይ የተበላሸ መሬት እንዲያገግም በማድረግና የአካባቢ ጥበቃና እንክብካቤን ለሀገራዊ ብልጽግና፣ ለአየር ንብረት ደህንነት እና ለግብርና መነቃቃት መሠረታዊ ለውጥ ተደርጎ ይወሰዳል።
ከደን ልማት አጀንዳው ስልታዊ ማዕቀፎች አንዱ በሆነው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብርም በየዓመቱ በክረምት ወቅት በሚሊየኖች የሚቆጠሩ ዜጎችን በማንቀሳቀስ በመላ ሀገሪቱ በቢሊየን የሚቆጠሩ ችግኞችን በስኬት መተከል ተችሏል።
በአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር ለሀገር በቀል ዛፎች ቅድሚያ መስጠት በችግኝ ጣቢያዎች ምርት ላይ ትልቅ ትኩረት አግኝቷል፡፡
ለተስማሚ ሥነ ምህዳር በየዓመቱ ከሚተከሉት ችግኞች የሀገር በቀል ዛፎች የአካባቢውን አየር ንብረት ለማሻሻል፣ የመሬት መሸርሸርን ለመከላከል እና የተፈጥሮ ውኃ ተፋሰሶችን ለመጠበቅ ታስበው የተመረጡ ናቸው።
መንግሥት የፍራፍሬ ችግኞች እንደ አቮካዶ፣ ማንጎ እና ፓፓያ ያሉ እና የእንስሳት መኖ እፅዋትን በስፋት እንዲተከሉ በማበረታታት እና አርሶ አደሮችን ከንግድ ሰንሰለቶች ጋር በማገናኘት ገቢያቸውን እንዲያሳድጉ እንዲሁም የቡና እና የአትክልትና ፍራፍሬ ወጪ ንግድን እንዲፋጠን በማድረግ ላይ ነው።
በደን መልሶ ማልማት በበጎ ፈቃድ የተከናወኑ በገንዘብ የማይለኩ አካባቢያዊ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ውጤቶች ተመዝግበዋል፡፡
በከፍተኛ ቦታዎች ላይ የተካሄደው ደን ልማት የከርሰ-ምድር ውኃ ክምችትን ያሻሻለ ሲሆን÷ እንደ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ባሉ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ግድቦች ላይ የሚያርፈውን የደለል ክምችት ቀንሶታል።
በቁልቁለታማና ኮረብታ ቦታዎች ላይ የተሰሩ እርከኖች እና የተተከሉ ዛፎች ለም አፈር እንዳይሸረሸር በመከላከል ለምግብ ምርት የሚሆን ለም መሬት እንዲጠበቅ ማድረግ አስችሏል።
በደን ልማት መነሻነት የማህበር እና የግል ችግኝ ጣቢያዎች መስፋፋት በተለይም ለወጣቶች ዘላቂ የሥራ ዕድሎችን የፈጠረ ነው።
ከዚህ በተጨማሪ የኢትዮጵያ የደን ልማት ጥረቶች የተባበሩት መንግሥታት የሥነ ምህዳር ማገገሚያ አስር ዓመት፣ የቦን ፈተና እና ሀገራዊ የካርቦን ቅነሳ ቃልኪዳኖችን ጨምሮ ከዓለም አቀፍ ማዕቀፎች ጋር በቀጥታ የሚጣጣሙ ናቸው።
በሰፊ የሕዝብ ንቅናቄ የበረሃማነትን ሒደት መመለስ እንደሚቻል በማስመስከር ኢትዮጵያ ለአፍሪካ እና ለዓለም አርአያ ሆና እያገለገለች ነው።
ይህ ዓለም አቀፍ መሪነት ያለው የደን ልማት እና የቀጣይ መንገድ የመደመር መንግሥት ለመጪው ትውልድ አረንጓዴ ሀገር ለማስረከብ ያለውን ቁርጠኝነት የሚያሳይ ነው።
በምሕረት ደምሴ
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 20፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ለብዙ ዓመታት ከፍተኛ የመሬት መሸርሸር ተደጋጋሚ ድርቅ እና የደን ሽፋን መሳሳት ለኢትዮጵያ ሥነ ምህዳራዊ ሚዛን እና የግብርና ምርታማነት ትልቅ አደጋ ደቅነው ቆይተዋል።
አሁን ግን የአረንጓዴ ልማትና የደን ሽፋን ንቅናቄ መልክዓ ምድርን እየለወጠ፤ በመላ ሀገሪቱ በተደረገ ስልታዊ አመራር ኢትዮጵያ የአካባቢ ጥበቃ ታሪኳን በአዲስ መልክ እየጻፈች ትገኛለች።
በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አነሳሽነት በተጀመረው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር እየተመራች ሀገሪቱ በዘመናዊ ታሪክ ውስጥ እጅግ ግዙፍ ከሆኑት ተፈጥሮ ተኮር መፍትሔዎች አንዱን እየተገበረች ትገኛለች::
ይህም በሚሊየን የሚቆጠር ሄክታር መሬት በማንሰራራት ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር አረንጓዴ ኢኮኖሚ መገንባት የሚያስችል ሲሆን ÷ ወደ አረንጓዴ መሪነት የሚያሸጋግረው የኢትዮጵያ የረጅም ጊዜ የአካባቢ ጥበቃ ግብ ግልጽ እና ለውጥ አምጪ ነው፡፡
እስከ ፈረንጆቹ 2030 ድረስ የሀገሪቱን የደን ሽፋን ወደ 30 በመቶ ማሳደግ እና ከ54 ሚሊየን ሄክታር በላይ የተበላሸ መሬት እንዲያገግም በማድረግና የአካባቢ ጥበቃና እንክብካቤን ለሀገራዊ ብልጽግና፣ ለአየር ንብረት ደህንነት እና ለግብርና መነቃቃት መሠረታዊ ለውጥ ተደርጎ ይወሰዳል።
ከደን ልማት አጀንዳው ስልታዊ ማዕቀፎች አንዱ በሆነው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብርም በየዓመቱ በክረምት ወቅት በሚሊየኖች የሚቆጠሩ ዜጎችን በማንቀሳቀስ በመላ ሀገሪቱ በቢሊየን የሚቆጠሩ ችግኞችን በስኬት መተከል ተችሏል።
በአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር ለሀገር በቀል ዛፎች ቅድሚያ መስጠት በችግኝ ጣቢያዎች ምርት ላይ ትልቅ ትኩረት አግኝቷል፡፡
ለተስማሚ ሥነ ምህዳር በየዓመቱ ከሚተከሉት ችግኞች የሀገር በቀል ዛፎች የአካባቢውን አየር ንብረት ለማሻሻል፣ የመሬት መሸርሸርን ለመከላከል እና የተፈጥሮ ውኃ ተፋሰሶችን ለመጠበቅ ታስበው የተመረጡ ናቸው።
መንግሥት የፍራፍሬ ችግኞች እንደ አቮካዶ፣ ማንጎ እና ፓፓያ ያሉ እና የእንስሳት መኖ እፅዋትን በስፋት እንዲተከሉ በማበረታታት እና አርሶ አደሮችን ከንግድ ሰንሰለቶች ጋር በማገናኘት ገቢያቸውን እንዲያሳድጉ እንዲሁም የቡና እና የአትክልትና ፍራፍሬ ወጪ ንግድን እንዲፋጠን በማድረግ ላይ ነው።
በደን መልሶ ማልማት በበጎ ፈቃድ የተከናወኑ በገንዘብ የማይለኩ አካባቢያዊ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ውጤቶች ተመዝግበዋል፡፡
በከፍተኛ ቦታዎች ላይ የተካሄደው ደን ልማት የከርሰ-ምድር ውኃ ክምችትን ያሻሻለ ሲሆን÷ እንደ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ባሉ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ግድቦች ላይ የሚያርፈውን የደለል ክምችት ቀንሶታል።
በቁልቁለታማና ኮረብታ ቦታዎች ላይ የተሰሩ እርከኖች እና የተተከሉ ዛፎች ለም አፈር እንዳይሸረሸር በመከላከል ለምግብ ምርት የሚሆን ለም መሬት እንዲጠበቅ ማድረግ አስችሏል።
በደን ልማት መነሻነት የማህበር እና የግል ችግኝ ጣቢያዎች መስፋፋት በተለይም ለወጣቶች ዘላቂ የሥራ ዕድሎችን የፈጠረ ነው።
ከዚህ በተጨማሪ የኢትዮጵያ የደን ልማት ጥረቶች የተባበሩት መንግሥታት የሥነ ምህዳር ማገገሚያ አስር ዓመት፣ የቦን ፈተና እና ሀገራዊ የካርቦን ቅነሳ ቃልኪዳኖችን ጨምሮ ከዓለም አቀፍ ማዕቀፎች ጋር በቀጥታ የሚጣጣሙ ናቸው።
በሰፊ የሕዝብ ንቅናቄ የበረሃማነትን ሒደት መመለስ እንደሚቻል በማስመስከር ኢትዮጵያ ለአፍሪካ እና ለዓለም አርአያ ሆና እያገለገለች ነው።
ይህ ዓለም አቀፍ መሪነት ያለው የደን ልማት እና የቀጣይ መንገድ የመደመር መንግሥት ለመጪው ትውልድ አረንጓዴ ሀገር ለማስረከብ ያለውን ቁርጠኝነት የሚያሳይ ነው።
በምሕረት ደምሴ
Comments