1 day ago
አንዶኒ ኢራኦላ የሊቨርፑል አሰልጣኝ ሆኖ ተሾመ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 26፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ስፔናዊው አሰልጣኝ አንዶኒ ኢራኦላ አርነ ስሎትን በመተካት የሊቨርፑል አሰልጣኝ በመሆን ተሾሟል፡፡
በቦርንማውዝ አስደናቂ ቡድን መገንባት የቻለው ኢራኦላ በአንፊልዱ ክለብ እስከ ፈረንጆቹ 2028 የሚያቆየውን ኮንትራት መፈረሙ ተገልጿል፡፡
አሰልጣኙ በቆይታው ቡድኑን ወደ አሸናፊነት የመመለስ ሃላፊነት ተጥሎበታል፡፡
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 26፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ስፔናዊው አሰልጣኝ አንዶኒ ኢራኦላ አርነ ስሎትን በመተካት የሊቨርፑል አሰልጣኝ በመሆን ተሾሟል፡፡
በቦርንማውዝ አስደናቂ ቡድን መገንባት የቻለው ኢራኦላ በአንፊልዱ ክለብ እስከ ፈረንጆቹ 2028 የሚያቆየውን ኮንትራት መፈረሙ ተገልጿል፡፡
አሰልጣኙ በቆይታው ቡድኑን ወደ አሸናፊነት የመመለስ ሃላፊነት ተጥሎበታል፡፡
2 days ago
(ዘ-ሐበሻ ስፖርት) ፈረንሳያዊው ተከላካይ ኢብራሂማ ኮናቴ ወደ ስፔኑ ታላቅ ክለብ ሪያል ማድሪድ የሚያደርገው ዝውውር መገባደጃው ላይ መድረሱን ምንጮች አረጋገጡ። ባለፉት 48 ሰዓታት ውስጥ በተደረጉት የድርድር ሒደቶች ከፍተኛ መሻሻል የታየ ሲሆን፣ በቅርቡ 27ኛ ዓመት የልደት በዓሉን ያከበረው ኮናቴ በአራት ዓመት ኮንትራት እና በፊርማ ክፍያ ጉዳዮች ላይ ከስምምነት ለመድረስ ጥቂት ዝርዝር ጉዳዮች ብቻ ቀርተውታል።
የማድሪድ ኃላፊዎች በፓሪስ የተወለደውን ይህንን ተከላካይ ለማስፈረም ከወራት በፊት ጀምሮ ፍላጎት ያሳዩ ቢሆንም፣ የተጫዋቹ ቀዳሚ ምርጫ ግን በሊቨርፑል መቆየት ነበር። ይሁን እንጂ ከክለቡ ጋር አዲስ ኮንትራት ለመፈራረም ባለመቻሉ፣ እ.ኤ.አ. በ2021 ከሌይፕዚግ ተነስቶ ያቀናበትን አንፊልድን በነጻ ዝውውር ለመልቀቅ ተገዷል።
ኮናቴ ሊቨርፑልን እንደሚለቅ በተረጋገጠበት ወቅት ሪያል ማድሪድ ፈጣን ጥያቄ በማቅረብ ቀዳሚው ቢሆንም፣ ባየር ሙኒክን፣ ባርሴሎናን እና የሳውዲ ክለቦችን ጨምሮ ሌሎች በርካታ ክለቦች የተከላካዩን ፊርማ ለማግኘት ጥረት አድርገው እንደነበር ምንጮች ጠቁመዋል።
ይህ ዝውውር ዕውን የሚሆን ከሆነ፣ ኮናቴ በሳንቲያጎ በርናባው ከሚገኙት የፈረንሳይ ብሔራዊ ቡድን አጋሮቹ ኪሊያን ምባፔ፣ ኦሬልየን ቹአሜኒ፣ ኤድዋርዶ ካማቪንጋ እና ፈርላንድ ሜንዲ ጋር ዳግም ይገናኛል። ተጫዋቹ በዓለማችን ትልቁን ክለብ ለመቀላቀል መቃረቡ እጅግ እንዳስደሰተው የተገለጸ ሲሆን፣ በቀጣዩ ሳምንት ከፈረንሳይ ብሔራዊ ቡድን ጋር ወደ ዓለም ዋንጫው ከማምራቱ በፊት የዝውውር ሒደቱ ሙሉ በሙሉ ተጠናቆ ማየት ይፈልጋል።
የማድሪድ ኃላፊዎች በፓሪስ የተወለደውን ይህንን ተከላካይ ለማስፈረም ከወራት በፊት ጀምሮ ፍላጎት ያሳዩ ቢሆንም፣ የተጫዋቹ ቀዳሚ ምርጫ ግን በሊቨርፑል መቆየት ነበር። ይሁን እንጂ ከክለቡ ጋር አዲስ ኮንትራት ለመፈራረም ባለመቻሉ፣ እ.ኤ.አ. በ2021 ከሌይፕዚግ ተነስቶ ያቀናበትን አንፊልድን በነጻ ዝውውር ለመልቀቅ ተገዷል።
ኮናቴ ሊቨርፑልን እንደሚለቅ በተረጋገጠበት ወቅት ሪያል ማድሪድ ፈጣን ጥያቄ በማቅረብ ቀዳሚው ቢሆንም፣ ባየር ሙኒክን፣ ባርሴሎናን እና የሳውዲ ክለቦችን ጨምሮ ሌሎች በርካታ ክለቦች የተከላካዩን ፊርማ ለማግኘት ጥረት አድርገው እንደነበር ምንጮች ጠቁመዋል።
ይህ ዝውውር ዕውን የሚሆን ከሆነ፣ ኮናቴ በሳንቲያጎ በርናባው ከሚገኙት የፈረንሳይ ብሔራዊ ቡድን አጋሮቹ ኪሊያን ምባፔ፣ ኦሬልየን ቹአሜኒ፣ ኤድዋርዶ ካማቪንጋ እና ፈርላንድ ሜንዲ ጋር ዳግም ይገናኛል። ተጫዋቹ በዓለማችን ትልቁን ክለብ ለመቀላቀል መቃረቡ እጅግ እንዳስደሰተው የተገለጸ ሲሆን፣ በቀጣዩ ሳምንት ከፈረንሳይ ብሔራዊ ቡድን ጋር ወደ ዓለም ዋንጫው ከማምራቱ በፊት የዝውውር ሒደቱ ሙሉ በሙሉ ተጠናቆ ማየት ይፈልጋል።
11 days ago
ሻምፒዮኑ አርሰናል ሲያሸንፍ፣ ዌስትሀም ወረደ ቶተንሀም ተረፈ
ከሁለት አስርት ዓመታት በላይ የዘለቀው የመድፈኞቹ የዋንጫ ጥማት ዛሬ በደመቀ ሁኔታ ተቋጭቷል።
አርሰናል በ38ኛው ሳምንት የመጨረሻ ጨዋታው ክሪስታል ፓላስን 2 ለ 1 በሆነ ውጤት በማሸነፍ የሊጉን የክብር አክሊል ይረከባል።
በመጀመሪያው የጨዋታ ክፍለ ጊዜ ገብርኤል ጀሱስ ያስቆጠራት ግብ የድሉን መንገድ የጠረገች ሲሆን፤ ቡድኑ እስከ ጨዋታው ፍጻሜ ድረስ ብቃቱን በማስመስከር የለንደን ጎዳናዎችን በደስታ እና በእልልታ እንዲሞሉ አድርጓል።
በሌሎች የዛሬው የመጨረሻ ሳምንት መርሃ ግብሮች ማንቸስተር ሲቲ በአስቶን ቪላ 2 ለ 1 በሆነ ውጤት ሲሸነፍ፣ ማንቸስተር ዩናይትድ ብራይተንን 3 ለ 0 በሆነ ሰፊ ውጤት ረቷል።
ዌስትሃም ሊድስን በ 3 ለ 0 በሆነ ውጤት ቢያሸንፍም ወደታችኛው ሊግ ወርዷል።
ቶተንሃም ኤቨርተንን 1 ለ 0 አሸንፎ በሊጉ መቆየት ችሏል።
በሌላ በኩል ሊቨርፑል ከብሬንትፎርድ ጋር 1 ለ 1፣ ፉልሃም ኒውካስትልን 2 ለ 0፣ ሰንደርላንድ ቼልሲን 2 ለ 1 በማሸነፍ ያልተጠበቀ ውጤት አስመዝግቧል።
በርንሌይ ከዎልቭስ እንዲሁም ኖቲንግሃም ፎረስት ከቦርንማውዝ ጋር 1 ለ 1 በሆነ አቻ ውጤት የውድድር ዘመኑን አጠናቀዋል።
Seledadotio
Seledadotio
ከሁለት አስርት ዓመታት በላይ የዘለቀው የመድፈኞቹ የዋንጫ ጥማት ዛሬ በደመቀ ሁኔታ ተቋጭቷል።
አርሰናል በ38ኛው ሳምንት የመጨረሻ ጨዋታው ክሪስታል ፓላስን 2 ለ 1 በሆነ ውጤት በማሸነፍ የሊጉን የክብር አክሊል ይረከባል።
በመጀመሪያው የጨዋታ ክፍለ ጊዜ ገብርኤል ጀሱስ ያስቆጠራት ግብ የድሉን መንገድ የጠረገች ሲሆን፤ ቡድኑ እስከ ጨዋታው ፍጻሜ ድረስ ብቃቱን በማስመስከር የለንደን ጎዳናዎችን በደስታ እና በእልልታ እንዲሞሉ አድርጓል።
በሌሎች የዛሬው የመጨረሻ ሳምንት መርሃ ግብሮች ማንቸስተር ሲቲ በአስቶን ቪላ 2 ለ 1 በሆነ ውጤት ሲሸነፍ፣ ማንቸስተር ዩናይትድ ብራይተንን 3 ለ 0 በሆነ ሰፊ ውጤት ረቷል።
ዌስትሃም ሊድስን በ 3 ለ 0 በሆነ ውጤት ቢያሸንፍም ወደታችኛው ሊግ ወርዷል።
ቶተንሃም ኤቨርተንን 1 ለ 0 አሸንፎ በሊጉ መቆየት ችሏል።
በሌላ በኩል ሊቨርፑል ከብሬንትፎርድ ጋር 1 ለ 1፣ ፉልሃም ኒውካስትልን 2 ለ 0፣ ሰንደርላንድ ቼልሲን 2 ለ 1 በማሸነፍ ያልተጠበቀ ውጤት አስመዝግቧል።
በርንሌይ ከዎልቭስ እንዲሁም ኖቲንግሃም ፎረስት ከቦርንማውዝ ጋር 1 ለ 1 በሆነ አቻ ውጤት የውድድር ዘመኑን አጠናቀዋል።
Seledadotio
Seledadotio
11 days ago
መድፉ ተተኮሰ
#ethiopia | የእንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ ፍጻሜ አርሰናል በድል ሲያጠናቅቅ ቶተንሃም በሊጉ መትረፉን አረጋግጧል ማንችስተር ሲቲ ደግሞ ሽንፈት አስተናግዷል
የ2025/26 የእንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ የውድድር ዘመን ዛሬ በአንድ ሰዓት በተደረጉ አስር ጨዋታዎች ፍጻሜውን አግኝቷል።
ከ22 ዓመታት ረጅም ጥበቃ በኋላ የሊጉን ዘውድ የደፋው አርሰናል ወደ ክሪስታል ፓላስ ሜዳ በመጓዝ 2 ለ 1 በሆነ ውጤት ማሸነፍ ችሏል።
ለመድፈኞቹ የማሸነፊያ ግቦቹን ያስቆጠሩት ጋብርኤል ጄሱስ እና ኖኒ ማዱኤኬ ሲሆኑ ክለቡ የዓመቱን ጉዞ በ85 ነጥብ በበላይነት አጠናቋል።
ወደ ታችኛው ክፍል የመውረድ ከፍተኛ ስጋት ውስጥ የነበረው ቶተንሃም ሆትስፐርስ ኤቨርተንን 1 ለ 0 በማሸነፍ በሊጉ መቆየቱን አረጋግጧል።
ለለንደኑ ክለብ ወሳኟን የህልውና ግብ ያስቆጠረው ጆአኦ ፓልሂንሃ ነው። በሌላ በኩል ላለመውረድ ሲፋለም የነበረው ዌስትሃም ዩናይትድ ሊድስ ዩናይትድን 3 ለ 0 ቢያሸንፍም ከውድድር መውረዱን ሊያስቀር አልቻለም።
ክለቡ ከቶተንሃም በሁለት ነጥብ በማነሱ ምክንያት በርንሌይ እና ዎልቭስን ተከትሎ ወደ ቻምፒየንሺፕ ወርዷል።
ከማንችስተር ሲቲ ጋር ለመለያየት የወሰነው አሰልጣኝ ፔፕ ጋርዲዮላ በመጨረሻው የሊግ ጨዋታው በአስቶንቪላ 2 ለ 1 በሆነ ውጤት ሽንፈት ገጥሞታል።
ታዋቂ ተጫዋቾቹን ሞሐመድ ሳላህ እና አንዲ ሮበርትሰንን በክብር ያሰናበተው ሊቨርፑል ከብሬንትፎርድ ጋር ያደረገውን ጨዋታ በአቻ ውጤት አጠናቋል።
ለአሰልጣኝ ማይክል ካሪክ የአንድ ዓመት ተጨማሪ ውል ያበረከተው ማንችስተር ዩናይትድ ብራይተንን ከሜዳው ውጪ 3 ለ 0 በሆነ ሰፊ ውጤት አሸንፏል።
በዚህ ጨዋታ ላይ አንድ ግብ አስቆጥሮ ለሌላው ደግሞ አመቻችቶ ያቀበለው ብሩኖ ፈርናንዴዝ አዲስ ታሪክ አስመዝግቧል። ፖርቹጋላዊው አማካይ በአንድ የውድድር ዓመት ውስጥ 21 ግብ የሆኑ ኳሶችን በማመቻቸት ቀዳሚው ተጫዋች መሆን ችሏል።
ወደ ሊጉ በቅርቡ ያደገው ሰንደርላንድ ቼልሲን 2 ለ 1 በማሸነፍ በቀጣዩ ዓመት በአውሮፓ መድረክ ላይ የመሳተፍ መብቱን አግኝቷል።
በተያያዙ ዜናዎች ፉልሃም ኒውካስትል ዩናይትድን 2 ለ 0 ሲያሸንፍ ኖቲንግሃም ፎረስት ከቦርንማውዝ ጋር 1 ለ 1 ተለያይቷል።
ቀድመው መውረዳቸውን ያረጋገጡት በርንሌይ እና ዎልቭስ ያደረጉት ጨዋታም በተመሳሳይ 1 ለ 1 በሆነ አቻ ውጤት ተጠናቋል።
#የእንግሊዝፕሪምየርሊግ #አርሰናል #ቶተንሃም #ማንችስተርሲቲ #ማንችስተርዩናይትድ #ሊቨርፑል #እግርኳስ #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | የእንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ ፍጻሜ አርሰናል በድል ሲያጠናቅቅ ቶተንሃም በሊጉ መትረፉን አረጋግጧል ማንችስተር ሲቲ ደግሞ ሽንፈት አስተናግዷል
የ2025/26 የእንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ የውድድር ዘመን ዛሬ በአንድ ሰዓት በተደረጉ አስር ጨዋታዎች ፍጻሜውን አግኝቷል።
ከ22 ዓመታት ረጅም ጥበቃ በኋላ የሊጉን ዘውድ የደፋው አርሰናል ወደ ክሪስታል ፓላስ ሜዳ በመጓዝ 2 ለ 1 በሆነ ውጤት ማሸነፍ ችሏል።
ለመድፈኞቹ የማሸነፊያ ግቦቹን ያስቆጠሩት ጋብርኤል ጄሱስ እና ኖኒ ማዱኤኬ ሲሆኑ ክለቡ የዓመቱን ጉዞ በ85 ነጥብ በበላይነት አጠናቋል።
ወደ ታችኛው ክፍል የመውረድ ከፍተኛ ስጋት ውስጥ የነበረው ቶተንሃም ሆትስፐርስ ኤቨርተንን 1 ለ 0 በማሸነፍ በሊጉ መቆየቱን አረጋግጧል።
ለለንደኑ ክለብ ወሳኟን የህልውና ግብ ያስቆጠረው ጆአኦ ፓልሂንሃ ነው። በሌላ በኩል ላለመውረድ ሲፋለም የነበረው ዌስትሃም ዩናይትድ ሊድስ ዩናይትድን 3 ለ 0 ቢያሸንፍም ከውድድር መውረዱን ሊያስቀር አልቻለም።
ክለቡ ከቶተንሃም በሁለት ነጥብ በማነሱ ምክንያት በርንሌይ እና ዎልቭስን ተከትሎ ወደ ቻምፒየንሺፕ ወርዷል።
ከማንችስተር ሲቲ ጋር ለመለያየት የወሰነው አሰልጣኝ ፔፕ ጋርዲዮላ በመጨረሻው የሊግ ጨዋታው በአስቶንቪላ 2 ለ 1 በሆነ ውጤት ሽንፈት ገጥሞታል።
ታዋቂ ተጫዋቾቹን ሞሐመድ ሳላህ እና አንዲ ሮበርትሰንን በክብር ያሰናበተው ሊቨርፑል ከብሬንትፎርድ ጋር ያደረገውን ጨዋታ በአቻ ውጤት አጠናቋል።
ለአሰልጣኝ ማይክል ካሪክ የአንድ ዓመት ተጨማሪ ውል ያበረከተው ማንችስተር ዩናይትድ ብራይተንን ከሜዳው ውጪ 3 ለ 0 በሆነ ሰፊ ውጤት አሸንፏል።
በዚህ ጨዋታ ላይ አንድ ግብ አስቆጥሮ ለሌላው ደግሞ አመቻችቶ ያቀበለው ብሩኖ ፈርናንዴዝ አዲስ ታሪክ አስመዝግቧል። ፖርቹጋላዊው አማካይ በአንድ የውድድር ዓመት ውስጥ 21 ግብ የሆኑ ኳሶችን በማመቻቸት ቀዳሚው ተጫዋች መሆን ችሏል።
ወደ ሊጉ በቅርቡ ያደገው ሰንደርላንድ ቼልሲን 2 ለ 1 በማሸነፍ በቀጣዩ ዓመት በአውሮፓ መድረክ ላይ የመሳተፍ መብቱን አግኝቷል።
በተያያዙ ዜናዎች ፉልሃም ኒውካስትል ዩናይትድን 2 ለ 0 ሲያሸንፍ ኖቲንግሃም ፎረስት ከቦርንማውዝ ጋር 1 ለ 1 ተለያይቷል።
ቀድመው መውረዳቸውን ያረጋገጡት በርንሌይ እና ዎልቭስ ያደረጉት ጨዋታም በተመሳሳይ 1 ለ 1 በሆነ አቻ ውጤት ተጠናቋል።
#የእንግሊዝፕሪምየርሊግ #አርሰናል #ቶተንሃም #ማንችስተርሲቲ #ማንችስተርዩናይትድ #ሊቨርፑል #እግርኳስ #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
Sponsored by
Surafel
11 days ago
(ዘ-ሐበሻ ስፖርት) በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ታሪክ ከባህር ማዶ መጥቶ እንደ ግብጹ "የአባይ ውሃ ዘመዳችን" መሀመድ ሳላህ የጎል መረብን ያንቀጠቀጠ የለም፤ 193 የማይታመኑ ጎሎች! ታሪኩ የሚጀምረው ነሐሴ 12 ቀን 2017 ነው። ሊቨርፑል ዋትፎርድን ሲገጥም፣ አሰልጣኝ የርገን ክሎፕ አዲስ ፈራሚውን «ወደ ፕሪሚየር ሊጉ እንኳን በደህና መጣህ!» በሚል አጭርና ግልጽ መልዕክት ወደ ሜዳ ሰደዱት። ያኔ የተጠነሰሰው አስፈሪው የሳላህ፣ ማኔ እና ፊርሚኖ የአጥቂ መስመር ጥምረት አሰልጣኝ ፔፕ ጋርዲዮላን ጭምር «ያናውጡኛል፣ አደገኞች ናቸው» እስኪል ድረስ ዓለምን ጉድ አሰኝቷል።
ሳላህ እና ማኔ የቅርብ ጓደኛሞች ባይሆኑም፣ በመካከላቸው የነበረው ጤናማ ውድድር እና ፊርሚኖ በሁለቱ መሀል የሚነሳውን እሳት በማጥፋት የተጫወተው ሚና፣ የሊቨርፑልን የድል ጉዞ የጀርባ አጥንት ሆኗል። የቡድኑ አጋሮቹ «ለእግር ኳስ የተፈጠረ» ብለው የሚመሰክሩለት ሳላህ፣ በምሳሌነት የሚመራ [ይላል] እና ለዝርዝር ነገሮች ከፍተኛ ትኩረት የሚሰጥ ጽኑ ተዋጊ ነው። ዋትፎርድን 5 ለ 0 ባሸነፉበት ጨዋታ ላይ፣ ጨዋታው እንደተጠናቀቀ ግብ ጠባቂውን ቤን ፎስተርን «ፍጹም ቅጣት ምት ቢሆን ኖሮ ወደየትኛው አቅጣጫ ትዘል ነበር?» ብሎ መጠየቁ ለስራው ያለውን ቁርጠኝነት ያሳያል።
በአንፊልድ ቆይታው አንዳንዴ ተስፋ መቁረጥ እና ቁጣ ታይቶበት ያውቃል። ባለፈው ታህሳስ ከዋና አሰልጣኙ አርኔ ስሎት ጋር የነበረው አለመግባባት አሁን ላለው ስንብት መነሻ ሆኗል። ይህ የውድድር ዘመን ለሊቨርፑል ስብስብ እጅግ ከባድ የነበረ ሲሆን፣ የቡድን አጋሩ ዲዮጎ ጆታ ህይወት ማለፍ ሳላህን ክፉኛ ጎድቶታል። «ከእረፍት በኋላ ወደ ሊቨርፑል መመለስ እንደዚህ ያስፈራኛል ብዬ አስቤ አውቅም» ሲል ሀዘኑን ገልጾ፣ በአንፊልድ ፊት እምባውን በማፍሰስ ሰብዓዊነቱን አሳይቷል።
በሜዳ ላይ ግን ሳላህ ከተፈጥሮ በላይ ነበር። በአንፊልድ የመጀመሪያ የውድድር ዘመኑ 58 የጎል ተሳትፎዎችን (በየ 71 ደቂቃው አንድ ጎል ላይ ተሳትፎ) በማድረግ ሜሲ እና ሮናልዶ ካሉበት ደረጃ ደርሷል። ማድሪድ ላይ ቶተንሃምን አሸንፈው የሻምፒዮንስ ሊግ ዋንጫ ሲያነሱ፣ በጉዲሰን ፓርክ ኤቨርተን ላይ የፑስካስ አዋርድ ያሸነፈባትን ጎል ሲያገባ፣ እና በኦልድ ትራፎርድ ማንችስተር ዩናይትድ ላይ ያሳየው ጀብዱ... ትዝታዎቹ ማለቂያ የላቸውም። የሲቲው አይሜሪክ ላፖርት ጭምር «ሳላህ በእኛ ላይ ሁልጊዜ እሳት ይተፋ ነበር፤ ለመከላከል ከገጠሙኝ ከባድ ተጫዋቾች አንዱ ነው» በማለት ይመሰክራል።
ሸሚዙን አውልቆ ደስታውን ሲገልጽም ሆነ በሱጁድ ፈጣሪውን ሲያመሰግን፣ የሳላህ ምስሎች መቼም አይረሱም። የቀድሞው አምበል ስቲቨን ጀራርድ «ቁጥሮቹ፣ ዋንጫዎቹ እና የገነባው ባህል የራሳቸው ታሪክ ይናገራሉ። መሀመድ ሳላህ በሁላችንም ዘንድ የተወደደ የክለቡ እውነተኛ ጀግና ነው» ሲል አወድሶታል። ትሬንት አሌክሳንደር አርኖልድም ለክለቡ ያላቸውን ዋጋ ሲገልጽ ሳላህን እና ጀራርድን በእኩልነት አንደኛ ደረጃ ላይ አስቀምጧቸዋል።
የ2024-25 የውድድር ዘመን ሊቨርፑል 20ኛውን የሊግ ዋንጫ ሲያነሳ፣ ሳላህ ከፍተኛ ጎል እና አሲስት በማድረግ በእንግሊዝ እግር ኳስ ታሪክ ውስጥ ደማቅ አሻራ አሳርፏል። አሁን ግን ሁሉም ነገር ፍጻሜ አለው። ከግብጽ የናይል ዴልታ የተነሳው የዚህ ድንቅ ተዋጊ ጉዞ፣ በሜርሲሳይድ አንፊልድ ላይ የማይረሳ ታሪክ ጽፎ ወደሚቀጥለው ምዕራፍ ተሸጋግሯል። የርገን ክሎፕ እንዳሉት፣ «ሲመጣ ሰዎች ምን እንደሚያስቡ ሳይሆን፣ ሲሄድ ምን እንደሚያስቡ ማወቁ ነው ትልቁ ነገር»። መሀመድ ሳላህ... ለአንፊልድ ትክክለኛው ተዋጊ፣ በትክክለኛው ጊዜ የመጣው ጀግና!
ሳላህ እና ማኔ የቅርብ ጓደኛሞች ባይሆኑም፣ በመካከላቸው የነበረው ጤናማ ውድድር እና ፊርሚኖ በሁለቱ መሀል የሚነሳውን እሳት በማጥፋት የተጫወተው ሚና፣ የሊቨርፑልን የድል ጉዞ የጀርባ አጥንት ሆኗል። የቡድኑ አጋሮቹ «ለእግር ኳስ የተፈጠረ» ብለው የሚመሰክሩለት ሳላህ፣ በምሳሌነት የሚመራ [ይላል] እና ለዝርዝር ነገሮች ከፍተኛ ትኩረት የሚሰጥ ጽኑ ተዋጊ ነው። ዋትፎርድን 5 ለ 0 ባሸነፉበት ጨዋታ ላይ፣ ጨዋታው እንደተጠናቀቀ ግብ ጠባቂውን ቤን ፎስተርን «ፍጹም ቅጣት ምት ቢሆን ኖሮ ወደየትኛው አቅጣጫ ትዘል ነበር?» ብሎ መጠየቁ ለስራው ያለውን ቁርጠኝነት ያሳያል።
በአንፊልድ ቆይታው አንዳንዴ ተስፋ መቁረጥ እና ቁጣ ታይቶበት ያውቃል። ባለፈው ታህሳስ ከዋና አሰልጣኙ አርኔ ስሎት ጋር የነበረው አለመግባባት አሁን ላለው ስንብት መነሻ ሆኗል። ይህ የውድድር ዘመን ለሊቨርፑል ስብስብ እጅግ ከባድ የነበረ ሲሆን፣ የቡድን አጋሩ ዲዮጎ ጆታ ህይወት ማለፍ ሳላህን ክፉኛ ጎድቶታል። «ከእረፍት በኋላ ወደ ሊቨርፑል መመለስ እንደዚህ ያስፈራኛል ብዬ አስቤ አውቅም» ሲል ሀዘኑን ገልጾ፣ በአንፊልድ ፊት እምባውን በማፍሰስ ሰብዓዊነቱን አሳይቷል።
በሜዳ ላይ ግን ሳላህ ከተፈጥሮ በላይ ነበር። በአንፊልድ የመጀመሪያ የውድድር ዘመኑ 58 የጎል ተሳትፎዎችን (በየ 71 ደቂቃው አንድ ጎል ላይ ተሳትፎ) በማድረግ ሜሲ እና ሮናልዶ ካሉበት ደረጃ ደርሷል። ማድሪድ ላይ ቶተንሃምን አሸንፈው የሻምፒዮንስ ሊግ ዋንጫ ሲያነሱ፣ በጉዲሰን ፓርክ ኤቨርተን ላይ የፑስካስ አዋርድ ያሸነፈባትን ጎል ሲያገባ፣ እና በኦልድ ትራፎርድ ማንችስተር ዩናይትድ ላይ ያሳየው ጀብዱ... ትዝታዎቹ ማለቂያ የላቸውም። የሲቲው አይሜሪክ ላፖርት ጭምር «ሳላህ በእኛ ላይ ሁልጊዜ እሳት ይተፋ ነበር፤ ለመከላከል ከገጠሙኝ ከባድ ተጫዋቾች አንዱ ነው» በማለት ይመሰክራል።
ሸሚዙን አውልቆ ደስታውን ሲገልጽም ሆነ በሱጁድ ፈጣሪውን ሲያመሰግን፣ የሳላህ ምስሎች መቼም አይረሱም። የቀድሞው አምበል ስቲቨን ጀራርድ «ቁጥሮቹ፣ ዋንጫዎቹ እና የገነባው ባህል የራሳቸው ታሪክ ይናገራሉ። መሀመድ ሳላህ በሁላችንም ዘንድ የተወደደ የክለቡ እውነተኛ ጀግና ነው» ሲል አወድሶታል። ትሬንት አሌክሳንደር አርኖልድም ለክለቡ ያላቸውን ዋጋ ሲገልጽ ሳላህን እና ጀራርድን በእኩልነት አንደኛ ደረጃ ላይ አስቀምጧቸዋል።
የ2024-25 የውድድር ዘመን ሊቨርፑል 20ኛውን የሊግ ዋንጫ ሲያነሳ፣ ሳላህ ከፍተኛ ጎል እና አሲስት በማድረግ በእንግሊዝ እግር ኳስ ታሪክ ውስጥ ደማቅ አሻራ አሳርፏል። አሁን ግን ሁሉም ነገር ፍጻሜ አለው። ከግብጽ የናይል ዴልታ የተነሳው የዚህ ድንቅ ተዋጊ ጉዞ፣ በሜርሲሳይድ አንፊልድ ላይ የማይረሳ ታሪክ ጽፎ ወደሚቀጥለው ምዕራፍ ተሸጋግሯል። የርገን ክሎፕ እንዳሉት፣ «ሲመጣ ሰዎች ምን እንደሚያስቡ ሳይሆን፣ ሲሄድ ምን እንደሚያስቡ ማወቁ ነው ትልቁ ነገር»። መሀመድ ሳላህ... ለአንፊልድ ትክክለኛው ተዋጊ፣ በትክክለኛው ጊዜ የመጣው ጀግና!
12 days ago
በፕሪሚየር ሊጉ ምርጡ የበላይነት ጊዜ የየትኛው ክለብ ነው?
#ethiopia | ማንቺስተር ዩናይትድ 1995-2001
የሰር አሌክስ ፌርጉሰን የመጀመሪያው ምርጡ ቡድን ነው።ቀያይ ሰይጣናቱ ከመጀመሪያ ዘጠኝ የፕሪሚየር ሊግ ዋንጫዎቻቸው ሰባቱን ያሳኩበት ነው።የ1998-99 የሶስትዮሽ ዋንጫን ያሳኩበት ውድድር አመት ደግሞ በምርጥነቱ የሚነሳው ነው።ግማሽ የሚሆነው የቡድን ስብስብ የተገኘው ደግሞ "ከclass of 92" ነው።እንደ ዴቪድ ቤካም ጋሪ እና ፊል ኔቭል ኒክ በት ሪያን ጊግስ እና ፖል ስኮልስ ያሉት ማለት ነው።
ኤሪክ ካንቶና ፒተር ሽማይክል ሮይ ኪን አንዲ ኮል እና ድዋይት ዮርክ በወቅቱ በቡድኑ ውስጥ የነበሩ ሌሎች ክዋክብት ተጫዋቾች ናቸው።
አርሰናል 2001-2004
የአርሰን ቬንገር አርሰናል የሰር አሌክስ ቡድንን በወጥነት ለሊጉ ዋንጫ ክብር መፎካከር የቻለ የመጀመሪያው ቡድን ነው።በ1997-98 እና 2001-02 የሁለትዮሽ ዋንጫን ክብር ያሳካ ሲሆን በ2003-04 ደግሞ "Invincible" ሆኖ ባለ ክብር ሆኗል።
ከ1999-2005 ስምንት ጊዜ ሁለተኛ ደረጃን በመያዝ አጠናቀዋል።በዚህ ቡድን ውስጥ ፈረንሳውያኑ ኮከቦች ቲዬሪ ሆነሪ ፖትሪክ ቪዬራ እና ሮበርት ፒሬዝ ሆላንዳዊው ጥበበኛ ዴኒስ ቤርካምፕ እንግሊዛውያኑ ተከላካዮች አሽሊ ኮል እና ሶል ካምቤል ከምርጦቹ መካከል ነበሩ።
ቼልሲ 2004-2007
ጆዜ ሞውሪንሆ በሰማያዊዮቹ ቤት በ2004 ከመጡ በኋላ የራሳቸውን ትልቁን አሻራ ማኖር የቻሉት በፍጥነት ነበር።
ራሳቸውን "The Special One" በማለት ለእንግሊዝ ሚዲያ ያስተዋወቁበት መንገድ ትልቁ የመነጋገሪያ ርዕስም ነበር።በመጀመሪያው ዙር ቆይታቸው ሁለት ጊዜ የሊጉን ዋንጫ ሲያነሱ በሶስተኛ የውድድር ዘመን የክለቡ ቆይታቸው ቡድናቸው ሁለተኛ ደረጃን ይዞ አጠናቋል።
በመጀመሪያ የውድድር አመት ቆይታቸው የሊጉን ዋንጫ ሲያሳኩ እስካሁን ያልተሰበሩ በርካታ ሪከርዶችን በመያዝ ነው።
እንግሊዛውያኑ ፍራንክ ላምፓርድ ጆን ቴሪ እና ጆ ኮል ግብ ጠባቂው ፔተር ቼክ የተከላካይ አማካዩ ክሎድ ማኬሌሌ እና አጥቂው ዲዲዬ ድሮግባ ከወርቃማው ቡድን ተጫዋቾች መካከል ዋነኞቹ ነበሩ።
ማንቺስተር ዩናይትድ ከ2006-2011
የፌርጉሰን ሁለተኛው ምርጡ ቡድን ነው።ለሶስት ተከታታይ የውድድር ዘመን የፕሪሚየር ሊጉን ዋንጫ ለማንሳት ከተሳነው በኋላም በአምስት አመት ውስጥ ለአራት ጊዜያት ያህል ባለ ክብር የሆነበት ነው።በ2007-08 ደግሞ የሻምፒየንስ ሊጉን ዋንጫ አሳክቷል።
ክርስቲያኖ ሮናልዶ እና ዌይን ሩኒ ግብ ጠባቂው ኤድዊን ቫንደርሳር አይረሴዎቹ የቡድኑ ቁልፍ ተጫዋቾች ነበሩ።
ማንቺስተር ሲቲ ከ2017-2024
በስተመጨረሻ የአሁኑን የጋርዲዮላ ቡድን እናገኛለን።በቶፕ ዲቪዥን ተከታታይ አራት የሊግ ክብሮችን በማሳካት የመጀመሪያው ቡድን ነው።በ2017- 18 100 ነጥቦችን በቀጣይ አመት ደግሞ 98 መሰብሰብ ችሏል። በ2022-23 የውድድር ዘመን የሶስትዮሽ ዋንጫን ክብር አሳክቷል። በዚህ ጊዜ የሲቲን የበላይነት ለመፈተን ጥረት ያደረገው ቡድን የየርገን ክሎፕ ሊቨርፑል ብቻ ነው ብሎ ማንሳት ይቻላል።
ኬቨን ዴብሩይነ ኤደርሰን በርናንዶ ሲልቫ ካይል ዎከር በልዩነት በዚህ ስኬታማ ጊዜ ውስጥ ስማቸው በትልቁ የሚነሳ ተጫዋቾች ናቸው።
(በሳምሶን አበበ)
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#ethiopia | ማንቺስተር ዩናይትድ 1995-2001
የሰር አሌክስ ፌርጉሰን የመጀመሪያው ምርጡ ቡድን ነው።ቀያይ ሰይጣናቱ ከመጀመሪያ ዘጠኝ የፕሪሚየር ሊግ ዋንጫዎቻቸው ሰባቱን ያሳኩበት ነው።የ1998-99 የሶስትዮሽ ዋንጫን ያሳኩበት ውድድር አመት ደግሞ በምርጥነቱ የሚነሳው ነው።ግማሽ የሚሆነው የቡድን ስብስብ የተገኘው ደግሞ "ከclass of 92" ነው።እንደ ዴቪድ ቤካም ጋሪ እና ፊል ኔቭል ኒክ በት ሪያን ጊግስ እና ፖል ስኮልስ ያሉት ማለት ነው።
ኤሪክ ካንቶና ፒተር ሽማይክል ሮይ ኪን አንዲ ኮል እና ድዋይት ዮርክ በወቅቱ በቡድኑ ውስጥ የነበሩ ሌሎች ክዋክብት ተጫዋቾች ናቸው።
አርሰናል 2001-2004
የአርሰን ቬንገር አርሰናል የሰር አሌክስ ቡድንን በወጥነት ለሊጉ ዋንጫ ክብር መፎካከር የቻለ የመጀመሪያው ቡድን ነው።በ1997-98 እና 2001-02 የሁለትዮሽ ዋንጫን ክብር ያሳካ ሲሆን በ2003-04 ደግሞ "Invincible" ሆኖ ባለ ክብር ሆኗል።
ከ1999-2005 ስምንት ጊዜ ሁለተኛ ደረጃን በመያዝ አጠናቀዋል።በዚህ ቡድን ውስጥ ፈረንሳውያኑ ኮከቦች ቲዬሪ ሆነሪ ፖትሪክ ቪዬራ እና ሮበርት ፒሬዝ ሆላንዳዊው ጥበበኛ ዴኒስ ቤርካምፕ እንግሊዛውያኑ ተከላካዮች አሽሊ ኮል እና ሶል ካምቤል ከምርጦቹ መካከል ነበሩ።
ቼልሲ 2004-2007
ጆዜ ሞውሪንሆ በሰማያዊዮቹ ቤት በ2004 ከመጡ በኋላ የራሳቸውን ትልቁን አሻራ ማኖር የቻሉት በፍጥነት ነበር።
ራሳቸውን "The Special One" በማለት ለእንግሊዝ ሚዲያ ያስተዋወቁበት መንገድ ትልቁ የመነጋገሪያ ርዕስም ነበር።በመጀመሪያው ዙር ቆይታቸው ሁለት ጊዜ የሊጉን ዋንጫ ሲያነሱ በሶስተኛ የውድድር ዘመን የክለቡ ቆይታቸው ቡድናቸው ሁለተኛ ደረጃን ይዞ አጠናቋል።
በመጀመሪያ የውድድር አመት ቆይታቸው የሊጉን ዋንጫ ሲያሳኩ እስካሁን ያልተሰበሩ በርካታ ሪከርዶችን በመያዝ ነው።
እንግሊዛውያኑ ፍራንክ ላምፓርድ ጆን ቴሪ እና ጆ ኮል ግብ ጠባቂው ፔተር ቼክ የተከላካይ አማካዩ ክሎድ ማኬሌሌ እና አጥቂው ዲዲዬ ድሮግባ ከወርቃማው ቡድን ተጫዋቾች መካከል ዋነኞቹ ነበሩ።
ማንቺስተር ዩናይትድ ከ2006-2011
የፌርጉሰን ሁለተኛው ምርጡ ቡድን ነው።ለሶስት ተከታታይ የውድድር ዘመን የፕሪሚየር ሊጉን ዋንጫ ለማንሳት ከተሳነው በኋላም በአምስት አመት ውስጥ ለአራት ጊዜያት ያህል ባለ ክብር የሆነበት ነው።በ2007-08 ደግሞ የሻምፒየንስ ሊጉን ዋንጫ አሳክቷል።
ክርስቲያኖ ሮናልዶ እና ዌይን ሩኒ ግብ ጠባቂው ኤድዊን ቫንደርሳር አይረሴዎቹ የቡድኑ ቁልፍ ተጫዋቾች ነበሩ።
ማንቺስተር ሲቲ ከ2017-2024
በስተመጨረሻ የአሁኑን የጋርዲዮላ ቡድን እናገኛለን።በቶፕ ዲቪዥን ተከታታይ አራት የሊግ ክብሮችን በማሳካት የመጀመሪያው ቡድን ነው።በ2017- 18 100 ነጥቦችን በቀጣይ አመት ደግሞ 98 መሰብሰብ ችሏል። በ2022-23 የውድድር ዘመን የሶስትዮሽ ዋንጫን ክብር አሳክቷል። በዚህ ጊዜ የሲቲን የበላይነት ለመፈተን ጥረት ያደረገው ቡድን የየርገን ክሎፕ ሊቨርፑል ብቻ ነው ብሎ ማንሳት ይቻላል።
ኬቨን ዴብሩይነ ኤደርሰን በርናንዶ ሲልቫ ካይል ዎከር በልዩነት በዚህ ስኬታማ ጊዜ ውስጥ ስማቸው በትልቁ የሚነሳ ተጫዋቾች ናቸው።
(በሳምሶን አበበ)
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
13 days ago
የራሱን ታሪክ የደገመው አርሰናል…
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 14፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) አርሰናል በስፔናዊው አሰልጣኝ ሚኬል አርቴታ እየተመራ የ2025/26 የውድድር ዓመት የሊጉ ሻምፒዮን መሆኑ ይታወቃል፡፡
ባለፉት ሦስት የውድድር ዓመታት በሊጉ ሁለተኛ ደረጃን ይዞ ያጠናቀቀው አርሰናል በዚህ ዓመት ሻምፒዮን በመሆን ከዚህ ቀደም ራሱ ፅፎት የነበረውን ታሪክ መድገም ችሏል፡፡
የሰሜን ለንደኑ ክለብ በ2022/23 እና በ2023/24 ማንቼስተር ሲቲን እንዲሁም አምና ሊቨርፑልን በመከተል በሁለተኛነት ማጠናቀቁ ይታወሳል፡፡
ከዚህ ቀደም አርሰናል በአሰልጣኝ አርሰን ቬንገር እየተመራ ለተከታታይ ሦስት የውድድር ዓመት 2ኛ ሆኖ ከጨረሰ በኋላ በአራተኛው የሊጉ ሻምፒዮን ሆኖ እንደነበር ይታወሳል፡፡
ከ1998/99 እስከ 2000/01 የውድድር ዓመት ድረስ ማንቼስተር ዩናይትድ ለተከታታይ ሦስት የውድድር ዓመት የሊጉ ሻምፒዮን ሲሆን አርሰናል 2ኛ ደረጃን ይዞ ማጠናቀቁ አይዘነጋም፡፡
በወቅቱ ለተከታታይ ሦስት የውድድር ዓመታት 2ኛ ደረጃን ይዞ ካጠናቀቀ በኋላ በአራተኛው የውድድር ዓመት (በ2001/02) የሊጉ ሻምፒዮን መሆን ችሏል፡፡
በወቅቱ አርሰናል ካደረጋቸው 38 ጨዋታዎች በ26ቱ አሸንፎ፣ 9 ጊዜ አቻ የተለያየ ሲሆን 3 ሽንፈት አስተናግዶ 87 ነጥብ በመሰብሰብ ነበር ሻምፒዮን የሆነው፡፡
መድፈኞቹ በስፔናዊው አሰልጣኝ ሚኬል አርቴታ እየተመሩ በዚህ ዓመት ያሳኩት የሊጉ ክብር በቀድሞው አሰልጣኛቸው አርሰን ቬንገር እየተመሩ ካሳኩት የሊጉ ዋንጫ ጋር አስገራሚ የታሪክ ግጥምጥሞሽ ፈጥሯል፡፡
አሰልጣኝ ሚኬል አርቴታ ባለፉት ሦስት ዓመታት ከመድፈኞቹ ጋር ዋንጫውን ማሳካት ባይችሉም የቀደሙት ዘመናት ታላቅነቱን በማይመጥን ሁኔታ ከዋንጫ ፉክክር ርቆ የቆየውን ክለብ ወደ ተፎካካሪነት በመመለስ ትልቅ ሥራ ሰርተዋል፡፡
በዚህ የውድድር ዓመት አንድ ጨዋታ እየቀረው ሻምፒዮን መሆኑን ያረጋገጠው አርሰናል ካደረጋቸው 37 ጨዋታዎች 25 ድል፣ 7 አቻ እና 5 ሽንፈት አስመዝግቧል፡፡
ሻምፒዮኑ አርሰናል የመጨረሻ ሳምንት ጨዋታውን የሚያሸንፍ ከሆነ በ2001/02 የውድድር ዓመት የሊጉ ሻምፒዮን ሲሆን ካሸነፈው 26 ጨዋታ ጋር በተመሳሳይ 26ኛ የሊግ ጨዋታ ድሉ ይሆናል፡፡
አርቴታ አርሰናልን ሲረከብ ቡድኑ ከሊጉ ዋንጫ መራቅ ብቻ ሳይሆን በአውሮፓ መድረክ የሚያሳትፈውን ቦታ ይዞ ለማጠናቀቅ የሚቸገር ቡድን ነበር፡፡
በአሰልጣኝ ሚኬል አርቴታ የቡድን ግንባታ ሒደት ከ22 ዓመታት በኋላ ከሊጉ ዋንጫ ጋር የተገናኙት መድፈኞቹ የፊታችን እሁድ ዋንጫውን በክብር ይቀበላሉ፡፡
በወንድማገኝ ጸጋዬ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 14፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) አርሰናል በስፔናዊው አሰልጣኝ ሚኬል አርቴታ እየተመራ የ2025/26 የውድድር ዓመት የሊጉ ሻምፒዮን መሆኑ ይታወቃል፡፡
ባለፉት ሦስት የውድድር ዓመታት በሊጉ ሁለተኛ ደረጃን ይዞ ያጠናቀቀው አርሰናል በዚህ ዓመት ሻምፒዮን በመሆን ከዚህ ቀደም ራሱ ፅፎት የነበረውን ታሪክ መድገም ችሏል፡፡
የሰሜን ለንደኑ ክለብ በ2022/23 እና በ2023/24 ማንቼስተር ሲቲን እንዲሁም አምና ሊቨርፑልን በመከተል በሁለተኛነት ማጠናቀቁ ይታወሳል፡፡
ከዚህ ቀደም አርሰናል በአሰልጣኝ አርሰን ቬንገር እየተመራ ለተከታታይ ሦስት የውድድር ዓመት 2ኛ ሆኖ ከጨረሰ በኋላ በአራተኛው የሊጉ ሻምፒዮን ሆኖ እንደነበር ይታወሳል፡፡
ከ1998/99 እስከ 2000/01 የውድድር ዓመት ድረስ ማንቼስተር ዩናይትድ ለተከታታይ ሦስት የውድድር ዓመት የሊጉ ሻምፒዮን ሲሆን አርሰናል 2ኛ ደረጃን ይዞ ማጠናቀቁ አይዘነጋም፡፡
በወቅቱ ለተከታታይ ሦስት የውድድር ዓመታት 2ኛ ደረጃን ይዞ ካጠናቀቀ በኋላ በአራተኛው የውድድር ዓመት (በ2001/02) የሊጉ ሻምፒዮን መሆን ችሏል፡፡
በወቅቱ አርሰናል ካደረጋቸው 38 ጨዋታዎች በ26ቱ አሸንፎ፣ 9 ጊዜ አቻ የተለያየ ሲሆን 3 ሽንፈት አስተናግዶ 87 ነጥብ በመሰብሰብ ነበር ሻምፒዮን የሆነው፡፡
መድፈኞቹ በስፔናዊው አሰልጣኝ ሚኬል አርቴታ እየተመሩ በዚህ ዓመት ያሳኩት የሊጉ ክብር በቀድሞው አሰልጣኛቸው አርሰን ቬንገር እየተመሩ ካሳኩት የሊጉ ዋንጫ ጋር አስገራሚ የታሪክ ግጥምጥሞሽ ፈጥሯል፡፡
አሰልጣኝ ሚኬል አርቴታ ባለፉት ሦስት ዓመታት ከመድፈኞቹ ጋር ዋንጫውን ማሳካት ባይችሉም የቀደሙት ዘመናት ታላቅነቱን በማይመጥን ሁኔታ ከዋንጫ ፉክክር ርቆ የቆየውን ክለብ ወደ ተፎካካሪነት በመመለስ ትልቅ ሥራ ሰርተዋል፡፡
በዚህ የውድድር ዓመት አንድ ጨዋታ እየቀረው ሻምፒዮን መሆኑን ያረጋገጠው አርሰናል ካደረጋቸው 37 ጨዋታዎች 25 ድል፣ 7 አቻ እና 5 ሽንፈት አስመዝግቧል፡፡
ሻምፒዮኑ አርሰናል የመጨረሻ ሳምንት ጨዋታውን የሚያሸንፍ ከሆነ በ2001/02 የውድድር ዓመት የሊጉ ሻምፒዮን ሲሆን ካሸነፈው 26 ጨዋታ ጋር በተመሳሳይ 26ኛ የሊግ ጨዋታ ድሉ ይሆናል፡፡
አርቴታ አርሰናልን ሲረከብ ቡድኑ ከሊጉ ዋንጫ መራቅ ብቻ ሳይሆን በአውሮፓ መድረክ የሚያሳትፈውን ቦታ ይዞ ለማጠናቀቅ የሚቸገር ቡድን ነበር፡፡
በአሰልጣኝ ሚኬል አርቴታ የቡድን ግንባታ ሒደት ከ22 ዓመታት በኋላ ከሊጉ ዋንጫ ጋር የተገናኙት መድፈኞቹ የፊታችን እሁድ ዋንጫውን በክብር ይቀበላሉ፡፡
በወንድማገኝ ጸጋዬ
14 days ago
(ዘ-ሐበሻ ስፖርት) የሳዑዲ አረቢያ እግር ኳስን በዓለም መድረክ ላይ ላስተዋወቀው የሊጉ "ፖስተር ቦይ" ከዚህ የተሻለ የድል ምስል ሊኖር አይችልም፦ ክርስቲያኖ ሮናልዶ የሳዑዲ ፕሮ ሊግን ዋንጫ ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ ላይ ከፍ አድርጎ አነሳው!
አል-ናስር በታህሳስ 2022 የማንቸስተር ዩናይትድን መልቀቅ ተከትሎ ይህንን ሜጋ ስታር ወደ ሪያድ ሲያመጣው፣ ዓለምን ማስደንገጥ እና ሀገሪቱን ወደ ዓለም አቀፉ የስፖርት መድረክ ማሸጋገር ዋነኛ ዓላማው ነበር። ይሁን እንጂ፣ ከሦስት ዓመታት በላይ ቆይታ በኋላ፣ ይህ የ41 ዓመቱ የእግር ኳስ ጠበብት አንድም ትልቅ የሀገር ውስጥ ዋንጫ አለማንሳቱ ብዙዎችን ሲያስገርም ቆይቷል።
የረዥም ጊዜ ጥበቃው ግን ሐሙስ ምሽት ማብቂያ አግኝቷል። በውድድር ዘመኑ የመጨረሻ ቀን፣ አል-ናስር ዳማክን 4ለ1 በረመረመበት አጓጊ ጨዋታ ላይ ሮናልዶ ሁለት ግቦችን በማስቆጠር፣ የዘመናት ባላንጣ የሆነውን አል-ሂላልን በመርታት ክለቡ ከ2019 ወዲህ ለመጀመሪያ ጊዜ የሻምፒዮንነት ክብሩን እንዲቀዳጅ አስችሎታል።
በቅርቡ በሳዑዲ ፕሮ ሊግ 100ኛ ግቡን ያስቆጠረው ሮናልዶ፣ በሁሉም ውድድሮች ለአል-ናስር 129 ግቦችን መረብ ላይ አሳርፏል። ይህ ዋንጫ ግን፣ እሱ በዋናነት እንዲያነሳው የተፈረመበት ትልቁ የክብር አክሊል ነበር።
ሮናልዶ ከሦስት ዓመት ተኩል በፊት ወደ ሳዑዲ ካመራ በኋላ ብዙ ነገሮች ተለውጠዋል። የእሱ መምጣት እንደ ካሪም ቤንዜማ፣ ንጎሎ ካንቴ፣ ሪያድ ማህሬዝ፣ ሳዲዮ ማኔ፣ ኔይማር እና ሌሎችም ታላላቅ ከዋክብት ወደ 'ታላላቆቹ አራት' ክለቦች (በሪያድ አል-ሂላል እና አል-ናስር፣ በጅዳ አል-አህሊ እና አል-ኢትሃድ) እንዲጎርፉ መንገድ ጠርጓል።
በ2023 ክረምት ላይ እነዚህ አራት ክለቦች በሀገሪቱ የህዝብ ኢንቨስትመንት ፈንድ (PIF) ስር የገቡ ሲሆን፣ በሚያዝያ 2026 ግን የ70 በመቶ የአል-ሂላል ድርሻ በልዑል አልዋሊድ ቢን ታላል ለሚመራው 'ኪንግደም ሆልዲንግ ኩባንያ' መሸጡ ይታወሳል።
ይህኛው የውድድር ዘመን ግን ከሁሉም የተለየ እና እጅግ አጓጊ ነበር። ለተወሰነ ጊዜ አራት ቡድኖች በዋንጫ ፉክክሩ ውስጥ ነበሩ። በአይቫን ቶኒ ግቦች የታገዘው አል-አህሊ፣ እና በሳዑዲው የነዳጅ ግዙፍ ኩባንያ አራምኮ የሚደገፈውና በብሬንዳን ሮጀርስ የሚሰለጥነው አል-ቃድሲያህ በመጨረሻዎቹ ሳምንታት ከፉክክሩ ርቀዋል።
ፉክክሩ በአል-ናስር እና በአል-ሂላል መካከል ብቻ ተወስኖ የቀጠለ ሲሆን፣ ሜይ 12 የተካሄደው የሁለቱ ክለቦች ትልቁ ፍጥጫ የሊጉን አቅጣጫ የወሰነ ነበር። ከ180 በላይ ሀገራት የተላለፈው ይህ ታሪካዊ ጨዋታ፣ አስገራሚ ፍጻሜ ነበረው። አል-ናስር 1ለ0 እየመራ ጨዋታው 97ኛው ደቂቃ ላይ ሲደርስ፣ ቢጫ የለበሱ ደጋፊዎች ድሉን ማክበር ጀምረው ነበር። ነገር ግን በመጨረሻዋ ሰከንድ ላይ ግብ ጠባቂው ቤንቶ በቀላሉ ሊይዛት የሚገባትን ኳስ አምልጦት በራሱ ላይ ባስቆጠረው ግብ ጨዋታው 1ለ1 ተጠናቀቀ። የዋንጫው ፉክክር ህያው ሆኖ ቢቀጥልም፣ ሐሙስ ዕለት ግን አል-ናስር ስራውን በተጨባጭ አጠናቋል።
ይህ ድል ለአል-ናስር 11ኛው የሊግ ዋንጫ ሲሆን፣ ለክርስቲያኖ ሮናልዶ ደግሞ በእንግሊዝ (ማንቸስተር ዩናይትድ)፣ በስፔን (ሪያል ማድሪድ) እና በጣሊያን (ጁቬንቱስ) ካነሳቸው ዋንጫዎች በመቀጠል 8ኛው የሊግ ሻምፒዮንነት ሆኖ ተመዝግቧል።
"በሪያድ ያሉ ባለስልጣናት የአል-ናስርን ድል የሮናልዶን ዝውውር እና ክለቡን በPIF ስር ለማቆየት የተደረገውን ውሳኔ ትክክለኛነት እንደሚያረጋግጥ አድርገው ይመለከቱታል" ሲሉ በፓሪስ ኢምሊዮን ቢዝነስ ስር የአፍሮ-ዩራሲያ ስፖርት ፕሮፌሰር የሆኑት ሳይመን ቻድዊክ ለቢቢሲ ተናግረዋል።
ይህ የሊግ ድል የመጣው፣ ቅዳሜ ዕለት የእስያ ዩሮፓ ሊግ አቻ በሆነው 'ኤኤፍሲ ቻምፒየንስ ሊግ 2' ፍጻሜ ላይ አል-ናስር ባልተጠበቀ ሁኔታ በጃፓኑ ጋምባ ኦሳካ ከተሸነፈ በኋላ በመሆኑ፣ ለሮናልዶ ትልቅ እፎይታን ሰጥቶታል።
የዘንድሮው የውድድር ዘመን ከውዝግብ የጸዳ አልነበረም። በየካቲት ወር ሮናልዶ በሁለት የሊግ ጨዋታዎች ላይ ያልተሰለፈ ሲሆን፣ ይህ የሆነው PIF ክለቡን የሚያስተዳድርበት መንገድ ከአል-ሂላል ጋር ሲነጻጸር ፍትሃዊ አይደለም በሚል ቅሬታ እንደሆነ ተዘግቧል። በሌላ በኩል ደግሞ ሊጉ ሮናልዶን ይደግፋል የሚሉ ወገኖች አልጠፉም። የአል-አህሊው አይቫን ቶኒ እና ብራዚላዊው ጋሌኖ ሊጉ ለሮናልዶ እና ለአል-ናስር ያደላል ሲሉ ከከሰሱት መካከል ይገኛሉ።
ሮናልዶ ለዚህ በሰጠው ምላሽ፡ "ይህ ለሊጉ ጥሩ አይመስለኝም። ሁሉም ያማርራል። ይህ እግር ኳስ እንጂ ጦርነት አይደለም... ግን ሁሉም ነገር አይፈቀድም። ብዙ፣ ብዙ መጥፎ ነገሮችን ስላየሁ በውድድር ዘመኑ መጨረሻ ላይ እናገራለሁ። ብዙ ተጫዋቾች በኢንስታግራም እና ፌስቡክ ላይ ስለ ዳኞች፣ ስለ ሊጉ እና ስለ ፕሮጀክቱ ቅሬታ ያሰማሉ። ይህ ጥሩ አይደለም፤ የሊጉም ዓላማ ይህ አይደለም" በማለት ተችቷል።
በአጠቃላይ የሳዑዲ አረቢያ የስፖርት ፕሮጀክት በቅርቡ ጥያቄ ውስጥ ወድቋል። ሚያዝያ ላይ PIF የሊቭ ጎልፍ የገንዘብ ድጋፍን እንደሚያቋርጥ ሲያሳውቅ፣ በጥር ወር ደግሞ ሀገሪቱ ልታስተናግደው የነበረው የ2029 የክረምት የእስያ ጨዋታዎች ላልተወሰነ ጊዜ ተራዝሟል። የሴቶች ቴኒስ የፍጻሜ ውድድርም ከሳዑዲ እንደሚወጣ ተዘግቧል።
በእግር ኳሱም ቢሆን ሚዲያው በታላላቅ ተጫዋቾች ዝውውር ወሬ ይሞላበት የነበረው ጊዜ ያለፈ ይመስላል። አሁንም ቢሆን አል-ቃድሲያህ ጣሊያናዊውን ማቴዎ ሬቴጉዊን በ57 ሚሊዮን ፓውንድ፣ አል-ሂላል ደግሞ ዳርዊን ኑኔዝን በ46 ሚሊዮን ፓውንድ ማስፈረማቸው ትልቅ እርምጃ ቢሆንም፣ ከ2023ቱ የዝውውር ማዕበል ጋር ሲነጻጸር አሁን ትኩረቱ ዳግም ሊሸጡ በሚችሉ ወጣት ተጫዋቾች ላይ ሆኗል። ይሁን እንጂ፣ ሊቨርፑልን የሚለቀቀውን ሞሀመድ ሳላህን የመሰለ አንጋፋ ኮከብ ለማምጣት አሁንም በጀቱ ክፍት መሆኑ ይነገራል።
የሮናልዶ የሊግ ሻምፒዮንነት የሳዑዲ ክለቦች በአንድ የዝውውር መስኮት 700 ሚሊዮን ፓውንድ ያፈሱበት "ያለፈው ወርቃማ ዘመን የመጨረሻው የድል ጩኸት" ተደርጎ ሊወሰድ ይችላል። ቀጣዩ የሳዑዲ እግር ኳስ እርምጃ ምን ሊሆን እንደሚችል የጊዜ ጉዳይ ቢሆንም፣ ለአሁኑ ግን የሪያድ ቢጫ ለባሾች እና የዓለም አቀፉ የሮናልዶ ደጋፊዎች በደስታ ማዕበል ውስጥ እየዋኙ ይገኛሉ።
አል-ናስር በታህሳስ 2022 የማንቸስተር ዩናይትድን መልቀቅ ተከትሎ ይህንን ሜጋ ስታር ወደ ሪያድ ሲያመጣው፣ ዓለምን ማስደንገጥ እና ሀገሪቱን ወደ ዓለም አቀፉ የስፖርት መድረክ ማሸጋገር ዋነኛ ዓላማው ነበር። ይሁን እንጂ፣ ከሦስት ዓመታት በላይ ቆይታ በኋላ፣ ይህ የ41 ዓመቱ የእግር ኳስ ጠበብት አንድም ትልቅ የሀገር ውስጥ ዋንጫ አለማንሳቱ ብዙዎችን ሲያስገርም ቆይቷል።
የረዥም ጊዜ ጥበቃው ግን ሐሙስ ምሽት ማብቂያ አግኝቷል። በውድድር ዘመኑ የመጨረሻ ቀን፣ አል-ናስር ዳማክን 4ለ1 በረመረመበት አጓጊ ጨዋታ ላይ ሮናልዶ ሁለት ግቦችን በማስቆጠር፣ የዘመናት ባላንጣ የሆነውን አል-ሂላልን በመርታት ክለቡ ከ2019 ወዲህ ለመጀመሪያ ጊዜ የሻምፒዮንነት ክብሩን እንዲቀዳጅ አስችሎታል።
በቅርቡ በሳዑዲ ፕሮ ሊግ 100ኛ ግቡን ያስቆጠረው ሮናልዶ፣ በሁሉም ውድድሮች ለአል-ናስር 129 ግቦችን መረብ ላይ አሳርፏል። ይህ ዋንጫ ግን፣ እሱ በዋናነት እንዲያነሳው የተፈረመበት ትልቁ የክብር አክሊል ነበር።
ሮናልዶ ከሦስት ዓመት ተኩል በፊት ወደ ሳዑዲ ካመራ በኋላ ብዙ ነገሮች ተለውጠዋል። የእሱ መምጣት እንደ ካሪም ቤንዜማ፣ ንጎሎ ካንቴ፣ ሪያድ ማህሬዝ፣ ሳዲዮ ማኔ፣ ኔይማር እና ሌሎችም ታላላቅ ከዋክብት ወደ 'ታላላቆቹ አራት' ክለቦች (በሪያድ አል-ሂላል እና አል-ናስር፣ በጅዳ አል-አህሊ እና አል-ኢትሃድ) እንዲጎርፉ መንገድ ጠርጓል።
በ2023 ክረምት ላይ እነዚህ አራት ክለቦች በሀገሪቱ የህዝብ ኢንቨስትመንት ፈንድ (PIF) ስር የገቡ ሲሆን፣ በሚያዝያ 2026 ግን የ70 በመቶ የአል-ሂላል ድርሻ በልዑል አልዋሊድ ቢን ታላል ለሚመራው 'ኪንግደም ሆልዲንግ ኩባንያ' መሸጡ ይታወሳል።
ይህኛው የውድድር ዘመን ግን ከሁሉም የተለየ እና እጅግ አጓጊ ነበር። ለተወሰነ ጊዜ አራት ቡድኖች በዋንጫ ፉክክሩ ውስጥ ነበሩ። በአይቫን ቶኒ ግቦች የታገዘው አል-አህሊ፣ እና በሳዑዲው የነዳጅ ግዙፍ ኩባንያ አራምኮ የሚደገፈውና በብሬንዳን ሮጀርስ የሚሰለጥነው አል-ቃድሲያህ በመጨረሻዎቹ ሳምንታት ከፉክክሩ ርቀዋል።
ፉክክሩ በአል-ናስር እና በአል-ሂላል መካከል ብቻ ተወስኖ የቀጠለ ሲሆን፣ ሜይ 12 የተካሄደው የሁለቱ ክለቦች ትልቁ ፍጥጫ የሊጉን አቅጣጫ የወሰነ ነበር። ከ180 በላይ ሀገራት የተላለፈው ይህ ታሪካዊ ጨዋታ፣ አስገራሚ ፍጻሜ ነበረው። አል-ናስር 1ለ0 እየመራ ጨዋታው 97ኛው ደቂቃ ላይ ሲደርስ፣ ቢጫ የለበሱ ደጋፊዎች ድሉን ማክበር ጀምረው ነበር። ነገር ግን በመጨረሻዋ ሰከንድ ላይ ግብ ጠባቂው ቤንቶ በቀላሉ ሊይዛት የሚገባትን ኳስ አምልጦት በራሱ ላይ ባስቆጠረው ግብ ጨዋታው 1ለ1 ተጠናቀቀ። የዋንጫው ፉክክር ህያው ሆኖ ቢቀጥልም፣ ሐሙስ ዕለት ግን አል-ናስር ስራውን በተጨባጭ አጠናቋል።
ይህ ድል ለአል-ናስር 11ኛው የሊግ ዋንጫ ሲሆን፣ ለክርስቲያኖ ሮናልዶ ደግሞ በእንግሊዝ (ማንቸስተር ዩናይትድ)፣ በስፔን (ሪያል ማድሪድ) እና በጣሊያን (ጁቬንቱስ) ካነሳቸው ዋንጫዎች በመቀጠል 8ኛው የሊግ ሻምፒዮንነት ሆኖ ተመዝግቧል።
"በሪያድ ያሉ ባለስልጣናት የአል-ናስርን ድል የሮናልዶን ዝውውር እና ክለቡን በPIF ስር ለማቆየት የተደረገውን ውሳኔ ትክክለኛነት እንደሚያረጋግጥ አድርገው ይመለከቱታል" ሲሉ በፓሪስ ኢምሊዮን ቢዝነስ ስር የአፍሮ-ዩራሲያ ስፖርት ፕሮፌሰር የሆኑት ሳይመን ቻድዊክ ለቢቢሲ ተናግረዋል።
ይህ የሊግ ድል የመጣው፣ ቅዳሜ ዕለት የእስያ ዩሮፓ ሊግ አቻ በሆነው 'ኤኤፍሲ ቻምፒየንስ ሊግ 2' ፍጻሜ ላይ አል-ናስር ባልተጠበቀ ሁኔታ በጃፓኑ ጋምባ ኦሳካ ከተሸነፈ በኋላ በመሆኑ፣ ለሮናልዶ ትልቅ እፎይታን ሰጥቶታል።
የዘንድሮው የውድድር ዘመን ከውዝግብ የጸዳ አልነበረም። በየካቲት ወር ሮናልዶ በሁለት የሊግ ጨዋታዎች ላይ ያልተሰለፈ ሲሆን፣ ይህ የሆነው PIF ክለቡን የሚያስተዳድርበት መንገድ ከአል-ሂላል ጋር ሲነጻጸር ፍትሃዊ አይደለም በሚል ቅሬታ እንደሆነ ተዘግቧል። በሌላ በኩል ደግሞ ሊጉ ሮናልዶን ይደግፋል የሚሉ ወገኖች አልጠፉም። የአል-አህሊው አይቫን ቶኒ እና ብራዚላዊው ጋሌኖ ሊጉ ለሮናልዶ እና ለአል-ናስር ያደላል ሲሉ ከከሰሱት መካከል ይገኛሉ።
ሮናልዶ ለዚህ በሰጠው ምላሽ፡ "ይህ ለሊጉ ጥሩ አይመስለኝም። ሁሉም ያማርራል። ይህ እግር ኳስ እንጂ ጦርነት አይደለም... ግን ሁሉም ነገር አይፈቀድም። ብዙ፣ ብዙ መጥፎ ነገሮችን ስላየሁ በውድድር ዘመኑ መጨረሻ ላይ እናገራለሁ። ብዙ ተጫዋቾች በኢንስታግራም እና ፌስቡክ ላይ ስለ ዳኞች፣ ስለ ሊጉ እና ስለ ፕሮጀክቱ ቅሬታ ያሰማሉ። ይህ ጥሩ አይደለም፤ የሊጉም ዓላማ ይህ አይደለም" በማለት ተችቷል።
በአጠቃላይ የሳዑዲ አረቢያ የስፖርት ፕሮጀክት በቅርቡ ጥያቄ ውስጥ ወድቋል። ሚያዝያ ላይ PIF የሊቭ ጎልፍ የገንዘብ ድጋፍን እንደሚያቋርጥ ሲያሳውቅ፣ በጥር ወር ደግሞ ሀገሪቱ ልታስተናግደው የነበረው የ2029 የክረምት የእስያ ጨዋታዎች ላልተወሰነ ጊዜ ተራዝሟል። የሴቶች ቴኒስ የፍጻሜ ውድድርም ከሳዑዲ እንደሚወጣ ተዘግቧል።
በእግር ኳሱም ቢሆን ሚዲያው በታላላቅ ተጫዋቾች ዝውውር ወሬ ይሞላበት የነበረው ጊዜ ያለፈ ይመስላል። አሁንም ቢሆን አል-ቃድሲያህ ጣሊያናዊውን ማቴዎ ሬቴጉዊን በ57 ሚሊዮን ፓውንድ፣ አል-ሂላል ደግሞ ዳርዊን ኑኔዝን በ46 ሚሊዮን ፓውንድ ማስፈረማቸው ትልቅ እርምጃ ቢሆንም፣ ከ2023ቱ የዝውውር ማዕበል ጋር ሲነጻጸር አሁን ትኩረቱ ዳግም ሊሸጡ በሚችሉ ወጣት ተጫዋቾች ላይ ሆኗል። ይሁን እንጂ፣ ሊቨርፑልን የሚለቀቀውን ሞሀመድ ሳላህን የመሰለ አንጋፋ ኮከብ ለማምጣት አሁንም በጀቱ ክፍት መሆኑ ይነገራል።
የሮናልዶ የሊግ ሻምፒዮንነት የሳዑዲ ክለቦች በአንድ የዝውውር መስኮት 700 ሚሊዮን ፓውንድ ያፈሱበት "ያለፈው ወርቃማ ዘመን የመጨረሻው የድል ጩኸት" ተደርጎ ሊወሰድ ይችላል። ቀጣዩ የሳዑዲ እግር ኳስ እርምጃ ምን ሊሆን እንደሚችል የጊዜ ጉዳይ ቢሆንም፣ ለአሁኑ ግን የሪያድ ቢጫ ለባሾች እና የዓለም አቀፉ የሮናልዶ ደጋፊዎች በደስታ ማዕበል ውስጥ እየዋኙ ይገኛሉ።
19 days ago
አስቶን ቪላ ሊቨርፑልን በመርታት የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ውድድር ተሳትፎውን ማረጋገጥ ቻለ
#ethiopia | በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የ37ኛ ሳምንት መርሃ ግብር አስቶን ቪላ ሊቨርፑልን 4 ለ 2 በሆነ ውጤት አሸንፏል።
በቪላ ፓርክ ስታዲየም በተካሄደው በዚህ ጨዋታ ኦሊ ዋትኪንስ ሁለት ግቦችን ለአስቶን ቪላ ማስቆጠር የቻለ ሲሆን ሞርጋን ሮጀርስ እና ጆን ማክጊን ደግሞ ቀሪዎቹን ሁለት ጎሎች አክለዋል።
በአንጻሩ ለሊቨርፑል ሁለቱንም ግቦች ከመረብ ያሳረፈው ተከላካዩ ቨርጅል ቫን ዳይክ ነው።
በዚህ ጨዋታ ወሳኝ ሶስት ነጥብ ማግኘት የቻለው አስቶን ቪላ አጠቃላይ የነጥብ መጠኑን 62 በማድረስ በቀጣዩ የውድድር ዘመን በአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ መሳተፉን በይፋ አረጋግጧል።
#astonvilla #liverpool #epl #championsleague #footballnews #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የ37ኛ ሳምንት መርሃ ግብር አስቶን ቪላ ሊቨርፑልን 4 ለ 2 በሆነ ውጤት አሸንፏል።
በቪላ ፓርክ ስታዲየም በተካሄደው በዚህ ጨዋታ ኦሊ ዋትኪንስ ሁለት ግቦችን ለአስቶን ቪላ ማስቆጠር የቻለ ሲሆን ሞርጋን ሮጀርስ እና ጆን ማክጊን ደግሞ ቀሪዎቹን ሁለት ጎሎች አክለዋል።
በአንጻሩ ለሊቨርፑል ሁለቱንም ግቦች ከመረብ ያሳረፈው ተከላካዩ ቨርጅል ቫን ዳይክ ነው።
በዚህ ጨዋታ ወሳኝ ሶስት ነጥብ ማግኘት የቻለው አስቶን ቪላ አጠቃላይ የነጥብ መጠኑን 62 በማድረስ በቀጣዩ የውድድር ዘመን በአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ መሳተፉን በይፋ አረጋግጧል።
#astonvilla #liverpool #epl #championsleague #footballnews #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
Sponsored by
Surafel
19 days ago
ማንቼስተር ሲቲ ወይስ ቼልሲ - ተጠባቂው የፍጻሜ ጨዋታ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 8፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ማንቼስተር ሲቲን ከቼልሲ የሚያገናኘው የእንግሊዝ ኤፍ ኤ ካፕ የፍጻሜ ጨዋታ ዛሬ አመሻሽ 11 ሰዓት ላይ በዌምብሌይ ስታዲየም ይደረጋል፡፡
በአሰልጣኝ ፔፕ ጋርዲዮላ የሚመራው ማንቼስተር ሲቲ በግማሽ ፍጻሜው ሳውዛምፕተንን 2 ለ 1 በማሸነፍ ለፍጻሜ መብቃቱ ይታወሳል፡፡
ማንቼስተር ሲቲ የዘንድሮውን ጨምሮ ያለፉትን አራት ተከታታይ ዓመታት በኤፍ ኤ ካፕ የፍጻሜ ጨዋታ ላይ መገኘት ችሏል፡፡
ሆኖም ካለፉት ሦስት የኤፍ ኤ ካፕ የፍጻሜ ጨዋታዎች ማሸነፍ የቻለው አንዱን ብቻ ሲሆን፥ ለመጨረሻ ጊዜ የዋንጫው ባለቤት የሆነው በፈረንጆቹ 2023 ነበር፡፡
ማንቼስተር ሲቲ በታሪኩ ሰባት ጊዜ የኤፍ ኤ ካፕ ዋንጫን ማሳካት የቻለ ሲሆን፥ ለስምንተኛ ጊዜ ሻምፒዮን ለመሆን የሚያደርገው ፍልሚያ ይጠበቃል፡፡
አስቀድሞ የካራባኦ ዋንጫን ያሳካው ሲቲ በዚህ የውድድር ዓመት 2ኛ ዋንጫውን ፍለጋ ወደ ሜዳ ይገባል፡፡
በውድድር ዓመቱ የሦስትዮሽ ዋንጫ የማሳካት እድል ያለው ማንቼስተር ሲቲ ጉዞውን አጠናክሮ ለመቀጠል ይፋለማል፡፡
እስካሁን አሸናፊው ባልተለየበት የሊጉ የዋንጫ ፉክክር ውስጥ የሚገኘው ማንቼስተር ሲቲ ይህንን ዋንጫ ማሳካት ከቻለ የሦስትዮሽ ዋንጫ ጉዞውን እንደሚያጠናክርለት ይታመናል፡፡
ተጋጣሚው ቼልሲ በበኩሉ በግማሽ ፍጻሜው ሊድስ ዩናይትድን በኢንዞ ፈርናንዴዝ ብቸኛ ግብ በመርታት ለፍጻሜ መድረሱ አይዘነጋም፡፡
በታሪኩ ስምንት ጊዜ የኤፍ ኤ ዋንጫን ማሳካት የቻለው የምዕራብ ለንደኑ ክለብ ቼልሲ ለ9ኛ ጊዜ በመድረኩ ሻምፒዮን ለመሆን ይፋለማል፡፡
አሰልጣኞች ቢለዋውጥም መሻሻል ያልቻለው ቼልሲ የውድድር ዓመቱን ያለምንም ዋንጫ ላለማጠናቀቅ ብርቱ ፉክክር ያደርጋል ተብሎ ይጠበቃል፡፡
የምዕራብ ለንደኑ ክለብ ለመጨረሻ ጊዜ የኤፍ ኤ ዋንጫን ማሳካት የቻለው በፈረንጆቹ 2018 እንደነበር ይታወሳል፡፡
ከዚያ ወዲህ ቼልሲ በ2021 እና በ2022 የፍጻሜ ተፋላሚ መሆን ቢችልም ዋንጫውን ግን ማሳካት አልቻለም፡፡
በ1871/72 በጀመረው የእንግሊዝ ኤፍ ኤ ዋንጫ ውድድር አርሰናል 14 ጊዜ የዋንጫው ባለቤት በመሆን ቀዳሚው ሲሆን፥ ማንቼስተር ዩናይትድ 13 ጊዜ በመድረኩ ሻምፒዮን በመሆን ይከተላል፡፡
የዛሬ የፍጻሜ ተፋላሚው ቼልሲ፣ ሊቨርፑል እና ቶተንሃም ሆትስፐር በተመሳሳይ ስምንት ጊዜ ሻምፒዮን ሆነዋል፡፡
ሌላኛው የምሽቱ የፍጻሜ ተፋላሚ ማንቼስተር ሲቲ እንዲሁም አስቶንቪላ በተመሳሳይ ሰባት ጊዜ የኤፍ ኤ ዋንጫን በማንሳት በርካታ ጊዜ ሻምፒዮን ከሆኑ ቡድኖች መካከል ይጠቀሳሉ፡፡
በዌምብሌይ ስታዲየም አመሻሽ 11 ሰዓት ላይ የሚደረገውን ተጠባቂ የፍጻሜ ጨዋታ እንግሊዛዊው ዳኛ ዳረን ኢንግላንድ በመሐል ዳኝነት የሚመሩት ይሆናል፡፡
በወንድማገኝ ጸጋዬ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 8፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ማንቼስተር ሲቲን ከቼልሲ የሚያገናኘው የእንግሊዝ ኤፍ ኤ ካፕ የፍጻሜ ጨዋታ ዛሬ አመሻሽ 11 ሰዓት ላይ በዌምብሌይ ስታዲየም ይደረጋል፡፡
በአሰልጣኝ ፔፕ ጋርዲዮላ የሚመራው ማንቼስተር ሲቲ በግማሽ ፍጻሜው ሳውዛምፕተንን 2 ለ 1 በማሸነፍ ለፍጻሜ መብቃቱ ይታወሳል፡፡
ማንቼስተር ሲቲ የዘንድሮውን ጨምሮ ያለፉትን አራት ተከታታይ ዓመታት በኤፍ ኤ ካፕ የፍጻሜ ጨዋታ ላይ መገኘት ችሏል፡፡
ሆኖም ካለፉት ሦስት የኤፍ ኤ ካፕ የፍጻሜ ጨዋታዎች ማሸነፍ የቻለው አንዱን ብቻ ሲሆን፥ ለመጨረሻ ጊዜ የዋንጫው ባለቤት የሆነው በፈረንጆቹ 2023 ነበር፡፡
ማንቼስተር ሲቲ በታሪኩ ሰባት ጊዜ የኤፍ ኤ ካፕ ዋንጫን ማሳካት የቻለ ሲሆን፥ ለስምንተኛ ጊዜ ሻምፒዮን ለመሆን የሚያደርገው ፍልሚያ ይጠበቃል፡፡
አስቀድሞ የካራባኦ ዋንጫን ያሳካው ሲቲ በዚህ የውድድር ዓመት 2ኛ ዋንጫውን ፍለጋ ወደ ሜዳ ይገባል፡፡
በውድድር ዓመቱ የሦስትዮሽ ዋንጫ የማሳካት እድል ያለው ማንቼስተር ሲቲ ጉዞውን አጠናክሮ ለመቀጠል ይፋለማል፡፡
እስካሁን አሸናፊው ባልተለየበት የሊጉ የዋንጫ ፉክክር ውስጥ የሚገኘው ማንቼስተር ሲቲ ይህንን ዋንጫ ማሳካት ከቻለ የሦስትዮሽ ዋንጫ ጉዞውን እንደሚያጠናክርለት ይታመናል፡፡
ተጋጣሚው ቼልሲ በበኩሉ በግማሽ ፍጻሜው ሊድስ ዩናይትድን በኢንዞ ፈርናንዴዝ ብቸኛ ግብ በመርታት ለፍጻሜ መድረሱ አይዘነጋም፡፡
በታሪኩ ስምንት ጊዜ የኤፍ ኤ ዋንጫን ማሳካት የቻለው የምዕራብ ለንደኑ ክለብ ቼልሲ ለ9ኛ ጊዜ በመድረኩ ሻምፒዮን ለመሆን ይፋለማል፡፡
አሰልጣኞች ቢለዋውጥም መሻሻል ያልቻለው ቼልሲ የውድድር ዓመቱን ያለምንም ዋንጫ ላለማጠናቀቅ ብርቱ ፉክክር ያደርጋል ተብሎ ይጠበቃል፡፡
የምዕራብ ለንደኑ ክለብ ለመጨረሻ ጊዜ የኤፍ ኤ ዋንጫን ማሳካት የቻለው በፈረንጆቹ 2018 እንደነበር ይታወሳል፡፡
ከዚያ ወዲህ ቼልሲ በ2021 እና በ2022 የፍጻሜ ተፋላሚ መሆን ቢችልም ዋንጫውን ግን ማሳካት አልቻለም፡፡
በ1871/72 በጀመረው የእንግሊዝ ኤፍ ኤ ዋንጫ ውድድር አርሰናል 14 ጊዜ የዋንጫው ባለቤት በመሆን ቀዳሚው ሲሆን፥ ማንቼስተር ዩናይትድ 13 ጊዜ በመድረኩ ሻምፒዮን በመሆን ይከተላል፡፡
የዛሬ የፍጻሜ ተፋላሚው ቼልሲ፣ ሊቨርፑል እና ቶተንሃም ሆትስፐር በተመሳሳይ ስምንት ጊዜ ሻምፒዮን ሆነዋል፡፡
ሌላኛው የምሽቱ የፍጻሜ ተፋላሚ ማንቼስተር ሲቲ እንዲሁም አስቶንቪላ በተመሳሳይ ሰባት ጊዜ የኤፍ ኤ ዋንጫን በማንሳት በርካታ ጊዜ ሻምፒዮን ከሆኑ ቡድኖች መካከል ይጠቀሳሉ፡፡
በዌምብሌይ ስታዲየም አመሻሽ 11 ሰዓት ላይ የሚደረገውን ተጠባቂ የፍጻሜ ጨዋታ እንግሊዛዊው ዳኛ ዳረን ኢንግላንድ በመሐል ዳኝነት የሚመሩት ይሆናል፡፡
በወንድማገኝ ጸጋዬ
20 days ago
አስቶን ቪላ ሊቨርፑልን በማሸነፍ የአውሮፖ ሻምፒዮንስ ሊግ ተሳትፎን አረጋገጠ
**************
በ37ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ አስቶን ቪላ ሊቨርፑልን 4 ለ 2 አሸንፏል።
በቪላ ፓርክ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ ኦሊ ዋትኪንስ ሁለት ግቦችን ለአስቶን ቪላ ማስቆጠር የቻለ ሲሆን፣ ሞርጋን ሮጀርስ እና ጆን ማክጊን ቀሪዎቹን ሁለት ግቦች አስቆጥረዋል።
ቨርጅል ቫን ዳይክ በጨዋታው ለሊቨርፑል ሁለቱንም ግቦች ማስቆጠር ችሏል።
በጨዋታው ወሳኝ ሦስት ነጥብ ያገኘው አስቶን ቪላ ነጥቡን 62 በማድረስ በቀጣይ አመት በአውሮፖ ሻምፒዮንስ ሊግ መሳተፉን አረጋግጧል።
በዘረንቶስ ሰለሞን
#ebc #premierleague #football
**************
በ37ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ አስቶን ቪላ ሊቨርፑልን 4 ለ 2 አሸንፏል።
በቪላ ፓርክ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ ኦሊ ዋትኪንስ ሁለት ግቦችን ለአስቶን ቪላ ማስቆጠር የቻለ ሲሆን፣ ሞርጋን ሮጀርስ እና ጆን ማክጊን ቀሪዎቹን ሁለት ግቦች አስቆጥረዋል።
ቨርጅል ቫን ዳይክ በጨዋታው ለሊቨርፑል ሁለቱንም ግቦች ማስቆጠር ችሏል።
በጨዋታው ወሳኝ ሦስት ነጥብ ያገኘው አስቶን ቪላ ነጥቡን 62 በማድረስ በቀጣይ አመት በአውሮፖ ሻምፒዮንስ ሊግ መሳተፉን አረጋግጧል።
በዘረንቶስ ሰለሞን
#ebc #premierleague #football
20 days ago
አስቶን ቪላ ሊቨርፑልን በማሸነፍ አራተኛ ደረጃ ላይ ተቀመጠ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 7፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ 37ኛ ሳምንት መርሐ ግብር አስቶን ቪላ ሊቨርፑልን 4 ለ 2 አሸንፏል።
ምሽት 4 ሰዓት ላይ በቪላ ፓርክ ስታዲየም ሊቨርፑልን ያስተናገደው አስቶን ቪላ ሮጀርስ፣ ዋትኪንስ (ሁለት) እና ማክጊን ባስቆጠሯቸው ግቦች ድል አድርጓል።
የሊቨርፑልን ግቦች ቫን ዳይክ ከመረብ አሳርፏል።
በዚህም አስቶን ቪላ ነጥቡን 62 በማድረስ አራተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል።
ሊጉን አርሰናል በ79 ነጥብ እየመራ ሲሆን÷ ማንቼስተር ሲቲ በ77 ነጥብ ሁለተኛ፣ ማንቼስተር ዩናይትድ በ65 ነጥብ ሶስተኛ ደረጃን ይዘዋል።
ሊቨርፑል በ59 ነጥብ አምስተኛ ደረጃ ላይ ይገኛል።
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 7፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ 37ኛ ሳምንት መርሐ ግብር አስቶን ቪላ ሊቨርፑልን 4 ለ 2 አሸንፏል።
ምሽት 4 ሰዓት ላይ በቪላ ፓርክ ስታዲየም ሊቨርፑልን ያስተናገደው አስቶን ቪላ ሮጀርስ፣ ዋትኪንስ (ሁለት) እና ማክጊን ባስቆጠሯቸው ግቦች ድል አድርጓል።
የሊቨርፑልን ግቦች ቫን ዳይክ ከመረብ አሳርፏል።
በዚህም አስቶን ቪላ ነጥቡን 62 በማድረስ አራተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል።
ሊጉን አርሰናል በ79 ነጥብ እየመራ ሲሆን÷ ማንቼስተር ሲቲ በ77 ነጥብ ሁለተኛ፣ ማንቼስተር ዩናይትድ በ65 ነጥብ ሶስተኛ ደረጃን ይዘዋል።
ሊቨርፑል በ59 ነጥብ አምስተኛ ደረጃ ላይ ይገኛል።
20 days ago
ለ3ኛ ተከታታይ የውድድር ዓመት የፈረንሳይ ሊግ ሻምፒዮን - አሰልጣኝ ሉዊስ ኤንሪኬ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 7፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ስፔናዊው አሰልጣኝ ሉዊስ ኤንሪኬ ለተከታታይ 3ኛ የውድድር ዓመት ከፒኤስጂ ጋር የፈረንሳይ ሊግ ዋንጫን ማሸነፍ ችለዋል፡፡
በፈረንጆቹ 1970 ስፔን ውስጥ በዛሬው ዕለት የተወለዱት አሰልጣኝ ሉዊስ ኤንሪኬ የአሰልጣኝነት ስራቸውን የጀመሩት በባርሴሎና ቢ ቡድን ነው፡፡
ከባርሴሎና ቢ ቡድን በመቀጠል ሮማ እና ሴልታቪጎን ያሰለጠኑት አሰልጣኙ በፈረንጆቹ 2014 የባርሴሎና ዋናውን ቡድን ተረክበዋል፡፡
በካታላኑ ክለብ ባርሴሎና በነበራቸው የአሰልጣኝነት ቆይታ የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ፣ የስፔን ላሊጋ፣ የስፔን ሱፐር ካፕ፣ ኮፓ ዴል ሬይ፣ የዓለም ክለቦች ዋንጫ እና የአውሮፓ ሱፐር ካፕ ዋንጫዎችን አሳክተዋል፡፡
ከባርሴሎና ጋር ከተለያዩ በኋላ የስፔን ብሔራዊ ቡድንን ከፈረንጆቹ 2018 እስከ 2022 አሰልጥነው በ2023/24 ወደ ፈረንሳዩ ክለብ ፒኤስጂ አቅንተዋል፡፡
የፓሪሱን ክለብ በ2023/24 ከተረከቡ ወዲህ የዘንድሮን ጨምሮ ለተከታታይ ሦስት የውድድር ዓመታት የሊጉን ዋንጫ ማሳካት ችለዋል፡፡
ፒኤስጂ በታሪኩ 14ኛ የፈረንሳይ ሊግ ዋንጫውን ያሳካ ሲሆን÷ በኤንሪኬ እየተመራ ደግሞ ያለፉትን ሦስት ተከታታይ የውድድር ዓመት ሻምፒዮን ሆኗል፡፡
ፒኤስጂ በሀገር ውስጥ ውድድር ስኬታማ ቢሆንም በአውሮፓ መድረክ ግን ተፎካካሪ ለመሆን እና ዋንጫ ለማንሳት የኤንሪኬን ፓሪስ መድረስ ይፈልግ ነበር፡፡
ፒኤስጂ የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ዋንጫን ለማሳካት ሊዮኔል ሜሲ፣ ኔይማር ጁኒየር እና ኪሊያን ምባፔ የመሳሳሉ ተጫዋቾችን ቢያጣምርም ማሳካት እንዳልቻለ ይታወቃል፡፡
ከስፔናዊው አሰልጣኝ ሉዊስ ኤንሪኬ ፓሪስ መድረስ በኋላ ግን የክለቡ የዘመናት ጥያቄ ባሳለፍነው የውድድር ዘመን ምላሽ ማግኘቱ ይታወሳል፡፡
አሰልጣኝ ሉዊስ ኤንሪኬ የፈረንሳዩን ክለብ የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ የዘመናት ሕልም መፍታት የቻሉ ሰው ናቸው፡፡
ፒኤስጂ በታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ዋንጫን በፈረንጆቹ 2024/25 የውድድር ዓመት ሲያሳካ አሰልጣኝ ሉዊስ ኤንሪኬ በክለቡ ያመጡት ለውጥ ቀላል የሚባል አይደለም፡፡
አሰልጣኙ በአንድ ተጫዋች ላይ ጥገኛ ያልሆነ እንደ ቡድን የሚጫወት ጠንካራ ስብስብ በመገንባት ክለቡን ለዚህ ታላቅ ክብር አብቅተዋል፡፡
አሰልጣኝ ሉዊስ ኤንሪኬ አሁን የፈረንሳዩን ክለብ ፒኤስጂን በአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ መድረክ ለተከታታይ የውድድር ዓመት ለፍጻሜ ማድረስ ችለዋል፡፡
የአሰልጣኝ ኤንሪኬ ቡድን በዚህ የውድድር ዓመት በአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ተጋጣሚዎቹ ላይ 44 ግቦችን ያስቆጠረ ሲሆን÷ በዚህም በውድድር ዘመኑ በመድረኩ በርካታ ግቦችን በማስቆጠር ቀዳሚው ሆኗል።
ቡድኑ በዚህ የውድድር ዓመት በመድረኩ ባየርን ሙኒክ፣ ሊቨርፑል፣ ቼልሲ እና ባርሴሎናን የመሳሰሉ ቡድኖችን ማሸነፉ ይታወሳል፡፡
ፒኤስጂ በአሰልጣኝ ሉዊስ ኤንሪኬ እየተመራ ለተከታታይ የውድድር ዓመት የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ዋንጫን ያሳካ ይሆን የሚለው የሚጠበቅ ሲሆን÷ በፍጻሜው ከአርሰናል ጋር ጨዋታውን ያደርጋል፡፡
የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ የፍጻሜ ጨዋታ ግንቦት 22 ቀን 2018 ዓ.ም በሀንጋሪ ቡዳፔስት ፑሽካሽ አሬና ስታዲየም ይደረጋል።
በወንድማገኝ ጸጋዬ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 7፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ስፔናዊው አሰልጣኝ ሉዊስ ኤንሪኬ ለተከታታይ 3ኛ የውድድር ዓመት ከፒኤስጂ ጋር የፈረንሳይ ሊግ ዋንጫን ማሸነፍ ችለዋል፡፡
በፈረንጆቹ 1970 ስፔን ውስጥ በዛሬው ዕለት የተወለዱት አሰልጣኝ ሉዊስ ኤንሪኬ የአሰልጣኝነት ስራቸውን የጀመሩት በባርሴሎና ቢ ቡድን ነው፡፡
ከባርሴሎና ቢ ቡድን በመቀጠል ሮማ እና ሴልታቪጎን ያሰለጠኑት አሰልጣኙ በፈረንጆቹ 2014 የባርሴሎና ዋናውን ቡድን ተረክበዋል፡፡
በካታላኑ ክለብ ባርሴሎና በነበራቸው የአሰልጣኝነት ቆይታ የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ፣ የስፔን ላሊጋ፣ የስፔን ሱፐር ካፕ፣ ኮፓ ዴል ሬይ፣ የዓለም ክለቦች ዋንጫ እና የአውሮፓ ሱፐር ካፕ ዋንጫዎችን አሳክተዋል፡፡
ከባርሴሎና ጋር ከተለያዩ በኋላ የስፔን ብሔራዊ ቡድንን ከፈረንጆቹ 2018 እስከ 2022 አሰልጥነው በ2023/24 ወደ ፈረንሳዩ ክለብ ፒኤስጂ አቅንተዋል፡፡
የፓሪሱን ክለብ በ2023/24 ከተረከቡ ወዲህ የዘንድሮን ጨምሮ ለተከታታይ ሦስት የውድድር ዓመታት የሊጉን ዋንጫ ማሳካት ችለዋል፡፡
ፒኤስጂ በታሪኩ 14ኛ የፈረንሳይ ሊግ ዋንጫውን ያሳካ ሲሆን÷ በኤንሪኬ እየተመራ ደግሞ ያለፉትን ሦስት ተከታታይ የውድድር ዓመት ሻምፒዮን ሆኗል፡፡
ፒኤስጂ በሀገር ውስጥ ውድድር ስኬታማ ቢሆንም በአውሮፓ መድረክ ግን ተፎካካሪ ለመሆን እና ዋንጫ ለማንሳት የኤንሪኬን ፓሪስ መድረስ ይፈልግ ነበር፡፡
ፒኤስጂ የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ዋንጫን ለማሳካት ሊዮኔል ሜሲ፣ ኔይማር ጁኒየር እና ኪሊያን ምባፔ የመሳሳሉ ተጫዋቾችን ቢያጣምርም ማሳካት እንዳልቻለ ይታወቃል፡፡
ከስፔናዊው አሰልጣኝ ሉዊስ ኤንሪኬ ፓሪስ መድረስ በኋላ ግን የክለቡ የዘመናት ጥያቄ ባሳለፍነው የውድድር ዘመን ምላሽ ማግኘቱ ይታወሳል፡፡
አሰልጣኝ ሉዊስ ኤንሪኬ የፈረንሳዩን ክለብ የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ የዘመናት ሕልም መፍታት የቻሉ ሰው ናቸው፡፡
ፒኤስጂ በታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ዋንጫን በፈረንጆቹ 2024/25 የውድድር ዓመት ሲያሳካ አሰልጣኝ ሉዊስ ኤንሪኬ በክለቡ ያመጡት ለውጥ ቀላል የሚባል አይደለም፡፡
አሰልጣኙ በአንድ ተጫዋች ላይ ጥገኛ ያልሆነ እንደ ቡድን የሚጫወት ጠንካራ ስብስብ በመገንባት ክለቡን ለዚህ ታላቅ ክብር አብቅተዋል፡፡
አሰልጣኝ ሉዊስ ኤንሪኬ አሁን የፈረንሳዩን ክለብ ፒኤስጂን በአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ መድረክ ለተከታታይ የውድድር ዓመት ለፍጻሜ ማድረስ ችለዋል፡፡
የአሰልጣኝ ኤንሪኬ ቡድን በዚህ የውድድር ዓመት በአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ተጋጣሚዎቹ ላይ 44 ግቦችን ያስቆጠረ ሲሆን÷ በዚህም በውድድር ዘመኑ በመድረኩ በርካታ ግቦችን በማስቆጠር ቀዳሚው ሆኗል።
ቡድኑ በዚህ የውድድር ዓመት በመድረኩ ባየርን ሙኒክ፣ ሊቨርፑል፣ ቼልሲ እና ባርሴሎናን የመሳሰሉ ቡድኖችን ማሸነፉ ይታወሳል፡፡
ፒኤስጂ በአሰልጣኝ ሉዊስ ኤንሪኬ እየተመራ ለተከታታይ የውድድር ዓመት የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ዋንጫን ያሳካ ይሆን የሚለው የሚጠበቅ ሲሆን÷ በፍጻሜው ከአርሰናል ጋር ጨዋታውን ያደርጋል፡፡
የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ የፍጻሜ ጨዋታ ግንቦት 22 ቀን 2018 ዓ.ም በሀንጋሪ ቡዳፔስት ፑሽካሽ አሬና ስታዲየም ይደረጋል።
በወንድማገኝ ጸጋዬ
22 days ago
ማንቼስተር ሲቲ ከአርሰናል ጋር ያለውን የነጥብ ልዩነት አጠበበ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 5፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ተስተካካይ ጨዋታ ማንቼስተር ሲቲ ክሪስታል ፓላስን 3 ለ 0 አሸንፏል።
በዚህም ከሊጉ መሪ አርሰናል ጋር ያለውን የነጥብ ልዩነት ወደ ሁለት አጥብቧል።
ምሽት 4 ሰዓት ላይ በኢቲሃድ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ማንቼስተር ሲቲ ሴሜንዮ፣ ማርሙሽ እና ሳቪኒሆ ባስቆጠሯቸው ግቦች ክሪስታል ፓላስን በማሸነፍ የዋንጫ ፉክክር ውስጥ መቆየት ችሏል።
ሊጉን አርሰናል በ79 ነጥብ እየመራ ሲሆን÷ ማንቼስተር ሲቲ በ77 ነጥብ፣ ማንቼስተር ዩናይትድ በ65 እንዲሁም ሊቨርፑል በ59 ነጥብ ከ2ኛ እስከ 4ኛ ያለውን ደረጃ ይዘዋል።
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 5፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ተስተካካይ ጨዋታ ማንቼስተር ሲቲ ክሪስታል ፓላስን 3 ለ 0 አሸንፏል።
በዚህም ከሊጉ መሪ አርሰናል ጋር ያለውን የነጥብ ልዩነት ወደ ሁለት አጥብቧል።
ምሽት 4 ሰዓት ላይ በኢቲሃድ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ማንቼስተር ሲቲ ሴሜንዮ፣ ማርሙሽ እና ሳቪኒሆ ባስቆጠሯቸው ግቦች ክሪስታል ፓላስን በማሸነፍ የዋንጫ ፉክክር ውስጥ መቆየት ችሏል።
ሊጉን አርሰናል በ79 ነጥብ እየመራ ሲሆን÷ ማንቼስተር ሲቲ በ77 ነጥብ፣ ማንቼስተር ዩናይትድ በ65 እንዲሁም ሊቨርፑል በ59 ነጥብ ከ2ኛ እስከ 4ኛ ያለውን ደረጃ ይዘዋል።
Sponsored by
Surafel
22 days ago
ማንቼስተር ሲቲን በዋንጫ ፉክክር ውስጥ የሚያቆየው ወሳኝ ጨዋታ…
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 5፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ተስተካካይ ጨዋታ ማንቼስተር ሲቲ በኢቲሃድ ስታዲየም ከክሪስታል ፓላስ ጋር የሚያደርገው ፍልሚያ ይጠበቃል፡፡
ምሽት አራት ሰዓት ላይ በሚካሄደው በዚህ ጨዋታ ማንቼስተር ሲቲ በሊጉ የዋንጫ ፉክክር ውስጥ ለመቆየት ግጥሚያውን ማሸነፍ ይጠበቅበታል፡፡
ሲቲ የምሽቱን ጨዋታ ከተሸነፈ ወይም አቻ ከወጣ እንዲሁም አርሰናል በመጪው ሰኞ ከሊጉ መውረዱን ካረጋገጠው በርንሌይ የሚያደርገውን ጨዋታ ማሸነፍ ከቻለ የ2025/26 የውድድር ዘመን ሻምፒዮን መሆኑን ያረጋግጣል፡፡
አንድ ቀሪ ጨዋታ እያለው ከመሪው አርሰናል በአምስት ነጥብ አንሶ ሁለተኛ ደረጃ ላይ የሚገኘው ማንቼስተር ሲቲ÷ የምሽቱን ጨዋታ ካሸነፈ ልዩነቱን ወደ ሁለት በማጠበብ በሊጉ የዋንጫ ፉክክር ውስጥ የሚቆይ ይሆናል፡፡
ሊጉን አርሰናል በ79 ነጥብ እየመራ ሲሆን÷ ማንቼስተር ሲቲ በ74 ነጥብ፣ ማንቼስተር ዩናይትድ በ65 እንዲሁም ሊቨርፑል በ59 ነጥብ ከ2ኛ አስከ 4ኛ ደረጃ በመያዝ ይከተላሉ።
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 5፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ተስተካካይ ጨዋታ ማንቼስተር ሲቲ በኢቲሃድ ስታዲየም ከክሪስታል ፓላስ ጋር የሚያደርገው ፍልሚያ ይጠበቃል፡፡
ምሽት አራት ሰዓት ላይ በሚካሄደው በዚህ ጨዋታ ማንቼስተር ሲቲ በሊጉ የዋንጫ ፉክክር ውስጥ ለመቆየት ግጥሚያውን ማሸነፍ ይጠበቅበታል፡፡
ሲቲ የምሽቱን ጨዋታ ከተሸነፈ ወይም አቻ ከወጣ እንዲሁም አርሰናል በመጪው ሰኞ ከሊጉ መውረዱን ካረጋገጠው በርንሌይ የሚያደርገውን ጨዋታ ማሸነፍ ከቻለ የ2025/26 የውድድር ዘመን ሻምፒዮን መሆኑን ያረጋግጣል፡፡
አንድ ቀሪ ጨዋታ እያለው ከመሪው አርሰናል በአምስት ነጥብ አንሶ ሁለተኛ ደረጃ ላይ የሚገኘው ማንቼስተር ሲቲ÷ የምሽቱን ጨዋታ ካሸነፈ ልዩነቱን ወደ ሁለት በማጠበብ በሊጉ የዋንጫ ፉክክር ውስጥ የሚቆይ ይሆናል፡፡
ሊጉን አርሰናል በ79 ነጥብ እየመራ ሲሆን÷ ማንቼስተር ሲቲ በ74 ነጥብ፣ ማንቼስተር ዩናይትድ በ65 እንዲሁም ሊቨርፑል በ59 ነጥብ ከ2ኛ አስከ 4ኛ ደረጃ በመያዝ ይከተላሉ።
26 days ago
(ዘ-ሐበሻ ስፖርት) የፕሪሚየር ሊጉ የዋንጫ ፉክክር ወደ መጨረሻው እና ወሳኙ ምዕራፍ በተሸጋገረበት በዚህ ወቅት፣ ማንችስተር ሲቲ ማሸነፍ ግድ ይለው በነበረው ጨዋታ ብሬንትፎርድን በማንበርከክ የዋንጫ ተስፋውን አለምልሟል። ሰኞ እለት ከኤቨርተን ጋር 3 ለ 3 ተለያይተው ውድ ነጥብ ጥለው የነበሩት የፔፕ ጋርዲዮላ ልጆች፣ በሁለተኛው አጋማሽ ባስቆጠሯቸው ሶስት ግቦች የሊጉን መሪ አርሰናልን የነጥብ ልዩነት ወደ ሁለት ዝቅ ማድረግ ችለዋል። አሁን የሲቲ አይን ያረፈው፣ ሚካኤል አርቴታ የሚመራው አርሰናል እሁድ እለት ከመውረድ ስጋት ውስጥ ከሚገኘው ዌስትሃም ጋር በሚያደርገው ወሳኝ ጨዋታ ላይ ነው።
በሜዳው ላይ ልዩነት ፈጣሪ የነበረው ቤልጄሚያዊው ኮከብ ጀረሚ ዶኩ ነው። ገና በሁለተኛው ደቂቃ የብሬንትፎርዱን ግብ ጠባቂ ኩዊቪን ኬለኸርን የፈተነ ሙከራ ያደረገው ዶኩ፣ ብዙም ሳይቆይ ኤርሊንግ ሀላንድ በግንባር ገጭቶ ለሳተው ኳስም አመቻችቶ አቀብሎ ነበር። በመጀመሪያው አጋማሽ ሲቲዎች በርካታ ሙከራዎችን ቢያደርጉም ግብ ማስቆጠር ተስኗቸው በብስጭት ወደ መልበሻ ቤት አምርተዋል። ሀላንድ በቀጥታ በኬለኸር ላይ የሞከረው እና ክሪስቶፈር አየር ያዳነበት ኳስ የዚሁ ብስጭት ማሳያዎች ነበሩ።
ነገር ግን በ60ኛው ደቂቃ ላይ ያቺ የተጠበቀችው ወሳኝ ግብ ተቆጠረች። ጀረሚ ዶኩ ኳስን ወደ ውስጥ ይዞ በመግባት እጅግ ማራኪ በሆነ አጨራረስ የብሬንትፎርድን መረብ አናወጠ፤ ልክ ሰኞ እለት በኤቨርተን ላይ ቡድኑን ከሽንፈት በታደገበት አኳኋን! ከ15 ደቂቃዎች በኋላ (በ75ኛው ደቂቃ) ደግሞ ኤርሊንግ ሀላንድ በግፊያ ውስጥ ሁለተኛዋን ግብ በማስቆጠር የኢትሀድ ስታዲየምን ድባብ አቀለጠው። በጭማሪ ሰዓት (92ኛው ደቂቃ) ተቀይሮ የገባው ኦማር ማርሙሽ የሲቲን ሶስተኛ ግብ አክሎ የድሉን ሪቫን በቆረጠበት ሰዓት፣ ባለሜዳዎቹ ሙሉ ሶስት ነጥብ ማረጋገጥ ችለዋል።
ውጤቱ 3-0 ይሁን እንጂ እንግዳው ብሬንትፎርድ ቀላል ተጋጣሚ አልነበረም። የሲቲው ግብ ጠባቂ ጂያንሉዊጂ ዶናሩማ የጣሊያን ብሄራዊ ቡድን አምበልነቱን በሚመጥን ብቃት ቡድኑን ታድጓል። ማይክል ካዮዴ በረጅሙ የወረወረውን፣ ማቲያስ ጀንሰን ያሻማውን አደገኛ የቅጣት ምት፣ እንዲሁም ኢጎር ቲያጎ በሁለተኛው አጋማሽ በቅርብ ርቀት የሞከረውን ኳስ ዶናሩማ በሚገርም ቅልጥፍና አድኖታል። በዚህም ሲቲ መረቡን ሳያስደፍር ሲወጣ፣ ብሬንትፎርድ በሊጉ 8ኛ ደረጃ ላይ እንዲረጋ ሆኗል።
በእረፍት ሰዓት የሲቲ ደጋፊዎች በቡድኑ እንቅስቃሴ ቅሬታቸውን ሲያሰሙ ነበር። ነገር ግን ጋርዲዮላ ተጫዋቾቹን አነቃቅቶ በሁለተኛው አጋማሽ ባስቆጠሯቸው ግቦች አጓጊውን የዋንጫ ፉክክር ዳግም አሙቀውታል። አሁን ሲቲዎች ዋንጫውን ለማንሳት የአርሰናልን ነጥብ መጣል የሚጠብቁ ሲሆን፣ በቀጣይ ከክሪስታል ፓላስ እና በርንማውዝ ጋር የሚያደርጉትን ጨዋታ ማሸነፍ ግድ ይላቸዋል።
ይህ ድል ሲቲ በሜዳው ያለመሸነፍ ክብረ ወሰኑን ወደ 16 ጨዋታዎች ከፍ እንዲል አድርጎለታል (በነሐሴ ወር ከስፐርስ ከደረሰበት ሽንፈት ውጪ)። የሲቲ የግብ ልዩነት አሁን +40 የደረሰ ሲሆን፣ ከአርሰናል (+41) በአንድ ግብ ብቻ ዝቅ ብሏል። ተቀይሮ የገባው ፊል ፎደን ያደረገው ሙከራ በኬለኸር ባይድን ኖሮ የግብ ልዩነታቸውን እኩል ማድረግ በቻሉ ነበር። ይሁን እንጂ ዋናው ነገር ሶስቱ ነጥብ ነው።
አሰልጣኝ ኪዝ አንድሪውስ በመጀመሪያው የውድድር ዘመናቸው ጥሩ ስራ ቢሰሩም፣ አሁን ግን ቡድናቸው ከመጨረሻዎቹ 8 ጨዋታዎች ያሸነፈው አንዱን ብቻ ነው። በሊጉ 22 ግቦችን በማስቆጠር ሁለተኛ ደረጃ ላይ የሚገኘው አጥቂው ኢጎር ቲያጎም በዚህ ጨዋታ ላይ ከሀላንድ የተሻለ ተጽዕኖ መፍጠር አልቻለም።
ብሬንትፎርዶች በዕለቱ ዳኛ ማይክል ሳሊስበሪ ውሳኔዎች በእጅጉ ተበሳጭተዋል። በተለይም የሲቲው አምበል ቤርናርዶ ሲልቫ በመጀመሪያው አጋማሽ ናታን ኮሊንስ ላይ ላሳየው ጥቃት በቢጫ ካርድ ብቻ መታለፉ፣ እንዲሁም ማቲየስ ኑኔዝ በኬቪን ሻዴ ላይ የሰራቸው ሊሆኑ የሚችሉ ሁለት ጥፋቶች በቫር (VAR) ታይተው ምንም ሳይባል ማለፉ እንግዶቹን አስቆጥቷል። አሁን ብሬንትፎርድ ክሪስታል ፓላስን እና ሊቨርፑልን በሚገጥምባቸው ቀሪ ሁለት ጨዋታዎች ወደ አሸናፊነት በመመለስ የአውሮፓ ተሳትፎ ተስፋውን ለማለምለም እና ውድድር ዘመኑን በውበት ለማጠናቀቅ ይጥራል።
በሜዳው ላይ ልዩነት ፈጣሪ የነበረው ቤልጄሚያዊው ኮከብ ጀረሚ ዶኩ ነው። ገና በሁለተኛው ደቂቃ የብሬንትፎርዱን ግብ ጠባቂ ኩዊቪን ኬለኸርን የፈተነ ሙከራ ያደረገው ዶኩ፣ ብዙም ሳይቆይ ኤርሊንግ ሀላንድ በግንባር ገጭቶ ለሳተው ኳስም አመቻችቶ አቀብሎ ነበር። በመጀመሪያው አጋማሽ ሲቲዎች በርካታ ሙከራዎችን ቢያደርጉም ግብ ማስቆጠር ተስኗቸው በብስጭት ወደ መልበሻ ቤት አምርተዋል። ሀላንድ በቀጥታ በኬለኸር ላይ የሞከረው እና ክሪስቶፈር አየር ያዳነበት ኳስ የዚሁ ብስጭት ማሳያዎች ነበሩ።
ነገር ግን በ60ኛው ደቂቃ ላይ ያቺ የተጠበቀችው ወሳኝ ግብ ተቆጠረች። ጀረሚ ዶኩ ኳስን ወደ ውስጥ ይዞ በመግባት እጅግ ማራኪ በሆነ አጨራረስ የብሬንትፎርድን መረብ አናወጠ፤ ልክ ሰኞ እለት በኤቨርተን ላይ ቡድኑን ከሽንፈት በታደገበት አኳኋን! ከ15 ደቂቃዎች በኋላ (በ75ኛው ደቂቃ) ደግሞ ኤርሊንግ ሀላንድ በግፊያ ውስጥ ሁለተኛዋን ግብ በማስቆጠር የኢትሀድ ስታዲየምን ድባብ አቀለጠው። በጭማሪ ሰዓት (92ኛው ደቂቃ) ተቀይሮ የገባው ኦማር ማርሙሽ የሲቲን ሶስተኛ ግብ አክሎ የድሉን ሪቫን በቆረጠበት ሰዓት፣ ባለሜዳዎቹ ሙሉ ሶስት ነጥብ ማረጋገጥ ችለዋል።
ውጤቱ 3-0 ይሁን እንጂ እንግዳው ብሬንትፎርድ ቀላል ተጋጣሚ አልነበረም። የሲቲው ግብ ጠባቂ ጂያንሉዊጂ ዶናሩማ የጣሊያን ብሄራዊ ቡድን አምበልነቱን በሚመጥን ብቃት ቡድኑን ታድጓል። ማይክል ካዮዴ በረጅሙ የወረወረውን፣ ማቲያስ ጀንሰን ያሻማውን አደገኛ የቅጣት ምት፣ እንዲሁም ኢጎር ቲያጎ በሁለተኛው አጋማሽ በቅርብ ርቀት የሞከረውን ኳስ ዶናሩማ በሚገርም ቅልጥፍና አድኖታል። በዚህም ሲቲ መረቡን ሳያስደፍር ሲወጣ፣ ብሬንትፎርድ በሊጉ 8ኛ ደረጃ ላይ እንዲረጋ ሆኗል።
በእረፍት ሰዓት የሲቲ ደጋፊዎች በቡድኑ እንቅስቃሴ ቅሬታቸውን ሲያሰሙ ነበር። ነገር ግን ጋርዲዮላ ተጫዋቾቹን አነቃቅቶ በሁለተኛው አጋማሽ ባስቆጠሯቸው ግቦች አጓጊውን የዋንጫ ፉክክር ዳግም አሙቀውታል። አሁን ሲቲዎች ዋንጫውን ለማንሳት የአርሰናልን ነጥብ መጣል የሚጠብቁ ሲሆን፣ በቀጣይ ከክሪስታል ፓላስ እና በርንማውዝ ጋር የሚያደርጉትን ጨዋታ ማሸነፍ ግድ ይላቸዋል።
ይህ ድል ሲቲ በሜዳው ያለመሸነፍ ክብረ ወሰኑን ወደ 16 ጨዋታዎች ከፍ እንዲል አድርጎለታል (በነሐሴ ወር ከስፐርስ ከደረሰበት ሽንፈት ውጪ)። የሲቲ የግብ ልዩነት አሁን +40 የደረሰ ሲሆን፣ ከአርሰናል (+41) በአንድ ግብ ብቻ ዝቅ ብሏል። ተቀይሮ የገባው ፊል ፎደን ያደረገው ሙከራ በኬለኸር ባይድን ኖሮ የግብ ልዩነታቸውን እኩል ማድረግ በቻሉ ነበር። ይሁን እንጂ ዋናው ነገር ሶስቱ ነጥብ ነው።
አሰልጣኝ ኪዝ አንድሪውስ በመጀመሪያው የውድድር ዘመናቸው ጥሩ ስራ ቢሰሩም፣ አሁን ግን ቡድናቸው ከመጨረሻዎቹ 8 ጨዋታዎች ያሸነፈው አንዱን ብቻ ነው። በሊጉ 22 ግቦችን በማስቆጠር ሁለተኛ ደረጃ ላይ የሚገኘው አጥቂው ኢጎር ቲያጎም በዚህ ጨዋታ ላይ ከሀላንድ የተሻለ ተጽዕኖ መፍጠር አልቻለም።
ብሬንትፎርዶች በዕለቱ ዳኛ ማይክል ሳሊስበሪ ውሳኔዎች በእጅጉ ተበሳጭተዋል። በተለይም የሲቲው አምበል ቤርናርዶ ሲልቫ በመጀመሪያው አጋማሽ ናታን ኮሊንስ ላይ ላሳየው ጥቃት በቢጫ ካርድ ብቻ መታለፉ፣ እንዲሁም ማቲየስ ኑኔዝ በኬቪን ሻዴ ላይ የሰራቸው ሊሆኑ የሚችሉ ሁለት ጥፋቶች በቫር (VAR) ታይተው ምንም ሳይባል ማለፉ እንግዶቹን አስቆጥቷል። አሁን ብሬንትፎርድ ክሪስታል ፓላስን እና ሊቨርፑልን በሚገጥምባቸው ቀሪ ሁለት ጨዋታዎች ወደ አሸናፊነት በመመለስ የአውሮፓ ተሳትፎ ተስፋውን ለማለምለም እና ውድድር ዘመኑን በውበት ለማጠናቀቅ ይጥራል።
26 days ago
ማንቸስተር ሲቲ ብሬንትፎርድን በመርታት የዋንጫ ተፎካካሪነቱን አጠናከረ
#ethiopia | በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የ36ኛ ሳምንት መርሃ ግብር ማንቸስተር ሲቲ በገዛ ሜዳው ኢቲሃድ ስታዲየም ብሬንትፎርድን አስተናግዶ 3 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸንፏል።
ጨዋታው እስከ 60ኛው ደቂቃ ድረስ ያለምንም ግብ ቢቀጥልም በሁለተኛው አጋማሽ የሲቲ አጥቂዎች ባሳዩት ድንቅ ብቃት ድል ቀንቷቸዋል።
ለውሃ ሰማያዊዎቹ ግቦቹን ጄረሚ ዶኩ፣ አርሊንግ ሃላንድ እና ኦማር ማርሙሽ ከመረብ አሳርፈዋል።
ይህንን ውጤት ተከትሎ ማንቸስተር ሲቲ በሊጉ 22ኛ ድሉን በማስመዝገብ ነጥቡን ወደ 74 ከፍ አድርጓል።
ይህም ከመሪው አርሰናል ጋር ያለውን የነጥብ ልዩነት ወደ ሁለት ብቻ ዝቅ እንዲል አድርጎታል።
ኖርዌያዊው የግብ ማሽን አርሊንግ ሃላንድ በሊጉ ያስቆጠራቸውን ጎሎች ብዛት 25 በማድረስ ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነቱን በበላይነት እየመራ ይገኛል።
በሌላ በኩል በሊጉ መሪነት ላይ የሚገኘው አርሰናል ነገ ከዌስትሃም ዩናይትድ ጋር የሚያደርገው ጨዋታ በዋንጫ ፉክክሩ ላይ ትልቅ ተጽዕኖ ይኖረዋል ተብሎ ይጠበቃል።
ብሬንትፎርድ በበኩሉ በዚህ የውድድር ዓመት የ13ኛ ሽንፈቱን ያስተናገደ ሲሆን በ51 ነጥብ 8ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል።
በተያያዘ ዜና ማንቸስተር ዩናይትድ እና ሊቨርፑል በሳምንቱ መርሃ ግብራቸው ነጥብ መጋራታቸው ታውቋል።
#manchestercity #premierleague #footballnews #mancity #haaland #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የ36ኛ ሳምንት መርሃ ግብር ማንቸስተር ሲቲ በገዛ ሜዳው ኢቲሃድ ስታዲየም ብሬንትፎርድን አስተናግዶ 3 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸንፏል።
ጨዋታው እስከ 60ኛው ደቂቃ ድረስ ያለምንም ግብ ቢቀጥልም በሁለተኛው አጋማሽ የሲቲ አጥቂዎች ባሳዩት ድንቅ ብቃት ድል ቀንቷቸዋል።
ለውሃ ሰማያዊዎቹ ግቦቹን ጄረሚ ዶኩ፣ አርሊንግ ሃላንድ እና ኦማር ማርሙሽ ከመረብ አሳርፈዋል።
ይህንን ውጤት ተከትሎ ማንቸስተር ሲቲ በሊጉ 22ኛ ድሉን በማስመዝገብ ነጥቡን ወደ 74 ከፍ አድርጓል።
ይህም ከመሪው አርሰናል ጋር ያለውን የነጥብ ልዩነት ወደ ሁለት ብቻ ዝቅ እንዲል አድርጎታል።
ኖርዌያዊው የግብ ማሽን አርሊንግ ሃላንድ በሊጉ ያስቆጠራቸውን ጎሎች ብዛት 25 በማድረስ ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነቱን በበላይነት እየመራ ይገኛል።
በሌላ በኩል በሊጉ መሪነት ላይ የሚገኘው አርሰናል ነገ ከዌስትሃም ዩናይትድ ጋር የሚያደርገው ጨዋታ በዋንጫ ፉክክሩ ላይ ትልቅ ተጽዕኖ ይኖረዋል ተብሎ ይጠበቃል።
ብሬንትፎርድ በበኩሉ በዚህ የውድድር ዓመት የ13ኛ ሽንፈቱን ያስተናገደ ሲሆን በ51 ነጥብ 8ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል።
በተያያዘ ዜና ማንቸስተር ዩናይትድ እና ሊቨርፑል በሳምንቱ መርሃ ግብራቸው ነጥብ መጋራታቸው ታውቋል።
#manchestercity #premierleague #footballnews #mancity #haaland #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
26 days ago
ማንቼስተር ሲቲ ብሬንትፎርድን አሸነፈ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 1፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የ36ኛ ሳምንት መርሐግብር ማንቼስተር ሲቲ ብሬንትፎርድን 3 ለ 0 አሸንፏል፡፡
ምሽት 1 ሰዓት ከ30 በኢትሃድ በተደረገው ጨዋታ የውሃ ሰማያዊዎቹን ግቦች ዶኩ፣ ሀላንድ እና ማርሙሽ በ2ኛው አጋማሽ ከመረብ አሳርፈዋል፡፡
ውጤቱን ተከትሎ ማንቼስተር ሲቲ ነጥቡን 74 በማድረስ ከመሪው አርሰናል ጋር ያለውን የነጥብ ልዩነት ወደ ሁለት ማጥበብ ችሏል፡፡
ቀደም ሲል በተደረጉ የሊጉ ጨዋታዎች ማንቼስተር ዩናይትድ ከሰንድርላንድ 0 ለ 0፣ ሊቨርፑል ከቼልሲ 1 ለ 1 አቻ ሲለያዩ፥ ብራይተን ወልቭስን 3 ለ 0 እንዲሁም በርንማውዝ ፉልሃምን 1 ለ 0 አሸንፈዋል፡፡
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 1፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የ36ኛ ሳምንት መርሐግብር ማንቼስተር ሲቲ ብሬንትፎርድን 3 ለ 0 አሸንፏል፡፡
ምሽት 1 ሰዓት ከ30 በኢትሃድ በተደረገው ጨዋታ የውሃ ሰማያዊዎቹን ግቦች ዶኩ፣ ሀላንድ እና ማርሙሽ በ2ኛው አጋማሽ ከመረብ አሳርፈዋል፡፡
ውጤቱን ተከትሎ ማንቼስተር ሲቲ ነጥቡን 74 በማድረስ ከመሪው አርሰናል ጋር ያለውን የነጥብ ልዩነት ወደ ሁለት ማጥበብ ችሏል፡፡
ቀደም ሲል በተደረጉ የሊጉ ጨዋታዎች ማንቼስተር ዩናይትድ ከሰንድርላንድ 0 ለ 0፣ ሊቨርፑል ከቼልሲ 1 ለ 1 አቻ ሲለያዩ፥ ብራይተን ወልቭስን 3 ለ 0 እንዲሁም በርንማውዝ ፉልሃምን 1 ለ 0 አሸንፈዋል፡፡
26 days ago
ማንቼስተር ዩናይትድ ከሰንደርላንድ 0 - 0
ቦርንማውዝ ፉልሃምን 1 ለ 0
ብራይተን ወልቭስን 3 ለ 0
#ethiopia | በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የ36ኛ ሳምንት መርሃ ግብር ማንቼስተር ዩናይትድ ከሜዳው ውጭ ከሰንደርላንድ ጋር ያደረገው ጨዋታ ያለ ምንም ግብ በአቻ ውጤት ተጠናቋል።
ቀይ ሰይጣኖቹ ከሦስት ተከታታይ ድሎች በኋላ ነጥብ ለመጀመሪያ ጊዜ የተጋሩበት አጋጣሚ ሆኖ ተመዝግቧል።
በሌላ በኩል ቦርንማውዝ ፉልሃምን 1 ለ 0 በሆነ ውጤት በማሸነፍ በአውሮፓ መድረክ የመሳተፍ ተስፋውን አድሷል።
በዚህ ጨዋታ ከሁለቱም ወገን አንደርሰን እና ክሪስት በፈጸሙት ጥፋት በቀይ ካርድ ከሜዳ ተሰናብተዋል።
ብራይተን በበኩሉ ወልቭስን 3 ለ 0 በሆነ ሰፊ ውጤት ሲያሸንፍ ሂንሽልውድ፣ ሉዊስ ደንክ እና ያኩብ ሚንዝ የድል ግቦቹን ከመረብ አሳርፈዋል።
ቀደም ብሎ በአንፊልድ ስታዲየም የተደረገው የሊቨርፑል እና የቼልሲ ተጠባቂ ፍልሚያ 1 ለ 1 በሆነ አቻ ውጤት ተጠናቋል።
ለሊቨርፑል ራያን ግራቨንበርግ ግብ ሲያስቆጥር ለለንደኑ ክለብ ቼልሲ ደግሞ ኢንዞ ፈርናንዴዝ የአቻነቷን ግብ አስቆጥሯል።
ውጤቱ ቼልሲ ካጋጠሙት ተከታታይ ሽንፈቶች እንዲያገግም ሲረዳው ሊቨርፑል ግን በሻምፒዮንስ ሊግ ተሳትፎው ላይ ጥያቄ እንዲያንዣብብ አድርጎበታል።
#premierleague #footballnews #epl #sports #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
ቦርንማውዝ ፉልሃምን 1 ለ 0
ብራይተን ወልቭስን 3 ለ 0
#ethiopia | በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የ36ኛ ሳምንት መርሃ ግብር ማንቼስተር ዩናይትድ ከሜዳው ውጭ ከሰንደርላንድ ጋር ያደረገው ጨዋታ ያለ ምንም ግብ በአቻ ውጤት ተጠናቋል።
ቀይ ሰይጣኖቹ ከሦስት ተከታታይ ድሎች በኋላ ነጥብ ለመጀመሪያ ጊዜ የተጋሩበት አጋጣሚ ሆኖ ተመዝግቧል።
በሌላ በኩል ቦርንማውዝ ፉልሃምን 1 ለ 0 በሆነ ውጤት በማሸነፍ በአውሮፓ መድረክ የመሳተፍ ተስፋውን አድሷል።
በዚህ ጨዋታ ከሁለቱም ወገን አንደርሰን እና ክሪስት በፈጸሙት ጥፋት በቀይ ካርድ ከሜዳ ተሰናብተዋል።
ብራይተን በበኩሉ ወልቭስን 3 ለ 0 በሆነ ሰፊ ውጤት ሲያሸንፍ ሂንሽልውድ፣ ሉዊስ ደንክ እና ያኩብ ሚንዝ የድል ግቦቹን ከመረብ አሳርፈዋል።
ቀደም ብሎ በአንፊልድ ስታዲየም የተደረገው የሊቨርፑል እና የቼልሲ ተጠባቂ ፍልሚያ 1 ለ 1 በሆነ አቻ ውጤት ተጠናቋል።
ለሊቨርፑል ራያን ግራቨንበርግ ግብ ሲያስቆጥር ለለንደኑ ክለብ ቼልሲ ደግሞ ኢንዞ ፈርናንዴዝ የአቻነቷን ግብ አስቆጥሯል።
ውጤቱ ቼልሲ ካጋጠሙት ተከታታይ ሽንፈቶች እንዲያገግም ሲረዳው ሊቨርፑል ግን በሻምፒዮንስ ሊግ ተሳትፎው ላይ ጥያቄ እንዲያንዣብብ አድርጎበታል።
#premierleague #footballnews #epl #sports #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
26 days ago
ማንቼስተር ዩናይትድ እና ሰንደርላንድ አቻ ተለያዩ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 1፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ 36ኛ ሳምንት መርሐግብር ከሜዳው ውጭ ሰንደርላንድን የገጠመው ማንቼስተር ዩናይትድ ያለግብ አቻ ተለያይቷል።
በሌሎች ጨዋታዎች ብራይተን ወልቭስን 3 ለ 0 እንዲሁም በርንማውዝ ፉልሃምን 1 ለ 0 አሸንፈዋል፡፡
ቀደም ብሎ ቀን 8 ሰዓት ከ30 በተደረገ የሊጉ መርሐ ግብር ሊቨርፑል ከቼልሲ 1 ለ 1 አቻ ተለያይተዋል፡፡
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 1፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ 36ኛ ሳምንት መርሐግብር ከሜዳው ውጭ ሰንደርላንድን የገጠመው ማንቼስተር ዩናይትድ ያለግብ አቻ ተለያይቷል።
በሌሎች ጨዋታዎች ብራይተን ወልቭስን 3 ለ 0 እንዲሁም በርንማውዝ ፉልሃምን 1 ለ 0 አሸንፈዋል፡፡
ቀደም ብሎ ቀን 8 ሰዓት ከ30 በተደረገ የሊጉ መርሐ ግብር ሊቨርፑል ከቼልሲ 1 ለ 1 አቻ ተለያይተዋል፡፡
Sponsored by
Surafel
26 days ago
በሊጉ ዋንጫ ፉክክር ውስጥ ለመቆየትና ላለመውረድ የሚደረጉ ተጠባቂ ጨዋታዎች
የ36ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ዛሬ በሚደረጉ አምስት ጨዋታዎች መደረግ ይጀምራል፡፡
ቀን 8 ሰዓት 30 ላይ ሊቨርፑል በሜዳው አንፊልድ ሮድ ቼልሲን የሚያስተናግድበት መርሐ ግብር የዕለቱ ቀዳሚ ጨዋታ ነው፡፡
ሁለቱም ቡድኖች በአውሮፓ መድረክ የሚያሳትፋቸውን ውጤት ይዘው የውድድር ዓመቱን ለማጠናቀቅ እየተፋለሙ ይገኛል፡፡
በሊጉ ከሦስት ተከታታይ ድል በኋላ በሳምንቱ መጨረሻ በማንቼስተር ዩናይትድ ሽንፈት ያስተናገደው ሊቨርፑል ወደ ድል ለመመለስ ወደ ሜዳ ይገባል፡፡
ያለፉትን ስድስት ተከታታይ ጨዋታዎች በሊጉ የተሸነፈው ቼልሲ ወደ ድል ለመምጣት የሚያደርገው ፍልሚያ ይጠበቃል፡፡
ቼልሲ በዛሬው ጨዋታ በሊቨርፑል የሚሸነፍ ከሆነ ከ74 ዓመታት በኋላ ሰባት ተከታታይ የሊግ ጨዋታዎችን የሚሸነፍ ይሆናል፡፡
አመሻሽ 11 ሰዓት ላይ ማንቼስተር ዩናይትድ ከሜዳው ውጪ ተጉዞ ከሰንደርላንድ ጋር ጨዋታውን ያደርጋል፡፡
የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ተሳትፎውን ያረጋገጠው ማንቼስተር ዩናይትድ በሊጉ አራተኛ ተከታታይ ድሉን ለማሳካት ይፋለማል፡፡
በተመሳሳይ ሰዓት ፉልሃም ከቦርንማውዝ እንዲሁም ብራይተን ከወልቭስ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡
ምሽት 1 ሰዓት 30 ላይ ደጎሞ ማንቼስተር ሲቲ በሜዳው ኢትሃድ ከብሬንትፎርድ የሚያደርገው ጨዋታ ይጠበቃል፡፡
በ35ኛ ሳምንት የሊጉ መርሐ ግብር ነጥብ የጣለው ማንቼስተር ሲቲ የዋንጫ ፉክክሩን ለማስቀጠል ይፋለማል፡፡
ማንቼስተር ሲቲ የዛሬውን ጨዋታ የሚያሸንፍ ከሆነ አርሰናል ነገ ምሽት ጨዋታውን እስከሚያደርግ ድረስ የነጥብ ልዩነቱን ወደ ሁለት ማጥበብ ይችላል፡፡
seledadotio
seledadotio
የ36ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ዛሬ በሚደረጉ አምስት ጨዋታዎች መደረግ ይጀምራል፡፡
ቀን 8 ሰዓት 30 ላይ ሊቨርፑል በሜዳው አንፊልድ ሮድ ቼልሲን የሚያስተናግድበት መርሐ ግብር የዕለቱ ቀዳሚ ጨዋታ ነው፡፡
ሁለቱም ቡድኖች በአውሮፓ መድረክ የሚያሳትፋቸውን ውጤት ይዘው የውድድር ዓመቱን ለማጠናቀቅ እየተፋለሙ ይገኛል፡፡
በሊጉ ከሦስት ተከታታይ ድል በኋላ በሳምንቱ መጨረሻ በማንቼስተር ዩናይትድ ሽንፈት ያስተናገደው ሊቨርፑል ወደ ድል ለመመለስ ወደ ሜዳ ይገባል፡፡
ያለፉትን ስድስት ተከታታይ ጨዋታዎች በሊጉ የተሸነፈው ቼልሲ ወደ ድል ለመምጣት የሚያደርገው ፍልሚያ ይጠበቃል፡፡
ቼልሲ በዛሬው ጨዋታ በሊቨርፑል የሚሸነፍ ከሆነ ከ74 ዓመታት በኋላ ሰባት ተከታታይ የሊግ ጨዋታዎችን የሚሸነፍ ይሆናል፡፡
አመሻሽ 11 ሰዓት ላይ ማንቼስተር ዩናይትድ ከሜዳው ውጪ ተጉዞ ከሰንደርላንድ ጋር ጨዋታውን ያደርጋል፡፡
የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ተሳትፎውን ያረጋገጠው ማንቼስተር ዩናይትድ በሊጉ አራተኛ ተከታታይ ድሉን ለማሳካት ይፋለማል፡፡
በተመሳሳይ ሰዓት ፉልሃም ከቦርንማውዝ እንዲሁም ብራይተን ከወልቭስ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡
ምሽት 1 ሰዓት 30 ላይ ደጎሞ ማንቼስተር ሲቲ በሜዳው ኢትሃድ ከብሬንትፎርድ የሚያደርገው ጨዋታ ይጠበቃል፡፡
በ35ኛ ሳምንት የሊጉ መርሐ ግብር ነጥብ የጣለው ማንቼስተር ሲቲ የዋንጫ ፉክክሩን ለማስቀጠል ይፋለማል፡፡
ማንቼስተር ሲቲ የዛሬውን ጨዋታ የሚያሸንፍ ከሆነ አርሰናል ነገ ምሽት ጨዋታውን እስከሚያደርግ ድረስ የነጥብ ልዩነቱን ወደ ሁለት ማጥበብ ይችላል፡፡
seledadotio
seledadotio
26 days ago
ማንችስተር ሲቲ ከ ብሬንትፎርድ፣ ሊቨርፑል ከ ቼልሲ
*************
በ36ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬ ምሽት 1 ሰዓት ከ30 ላይ ማንችስተር ሲቲ ብሬንትፎርድን ያስተናግዳል። ከኤቨርተን ጋር ነጥብ መጋራቱን ተከትሎ የሊጉን ዋንጫ የማንሳት ዕድሉ ሙሉ በሙሉ ከእጁ የወጣው ማንችስተር ሲቲ፣ አሁንም ያለውን ጥቂት ዕድል ለመጠቀም እና በአርሰናል ላይ ጫና ለማሳደር ወደ ሜዳ ይገባል።
ሆኖም ዘንድሮ ጠንካራ የውድድር ጊዜ ያሳለፈው ብሬንትፎርድ፣ የአውሮፓ መድረክ ተሳትፎን ለማግኘት እየታገለ በመሆኑ ጨዋታው ለሲቲ እጅግ ፈታኝ እንደሚሆን ይጠበቃል። በተለይ ክሪስታል ፓላስ እና አስቶን ቪላ በዩሮፓ ሊግ እና በኮንፈረንስ ሊግ ለፍጻሜ መድረሳቸውን ተከትሎ፣ በቀጣይ ዓመት በአውሮፓ መድረክ የሚሳተፉ የእንግሊዝ ክለቦች ቁጥር ሊጨምር ስለሚችል በ51 ነጥብ 7ኛ ደረጃ ላይ የተቀመጠው ብሬንትፎርድ ይህንን አጋጣሚ ለመጠቀም ይፋለማል።
በኢትሃድ ስታዲየም በሚደረገው ጨዋታ ሮድሪ ለዛሬው ፍልሚያ ሊደርስ እንደሚችል አሰልጣኝ ፔፕ ጋርዲዮላ ተናግሯል። ጋርዲዮላ ትላንት በሰጠት መግለጫ "በዛሬው ጨዋታ ከተሸነፍን የዋንጫው ጉዞ በይፋ ያበቃል" ሲል የጨዋታውን ወሳኝነት ገልቷል። ሲቲ ካሸነፈ ከአርሰናል ያለውን የነጥብ ልዩነት ወደ ሁለት የሚያጠብ ይሆናል፡፡
ቀን 8 ሰዓት ከ30 ላይ ደግሞ ሊቨርፑል እና ቼልሲ የሚገናኙበት ጨዋታ ይጠበቃል። በፕሪሚየር ሊጉ ያለፉትን ስድስት ተከታታይ ጨዋታዎች የተሸነፈው ቼልሲ፣ ዛሬም በአንፊልድ ሌላ ከባድ ፈተና ይጠብቀዋል። ሊጉ ሊጠናቀቅ ሦስት ጨዋታዎች ብቻ እየቀሩት እስካሁን የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ተሳትፎውን ያላረጋገጠው ሊቨርፑል፣ ከዛሬው ጨዋታ ሦስት ነጥብ ካገኘ መሳተፉን በይፋ የሚያረጋግጥ ይሆናል። በአንፊልድ በሚደረገው ጨዋታ ሞሃመድ ሳላህ እና አሊሰን ቤከር አሁንም በጉዳት ከስብስቡ ውጭ ናቸው። በቼልሲ በኩል ሌቪ ኮልዊል እና ሬስ ጄምስ ለጨዋታው ሊደርሱ ይችላሉ ተብሏል።
በሻምፒዮንስ ሊግ መሳተፉን ቀድሞ ያረጋገጠመው ማንችስተር ዩናይትድ ከ ሜዳው ወጭ ከሰንደርላንድ 11 ሰዓት ላይ ጨዋታውን ያደርጋል፡፡ ብራይተን ከ ዎልቭስ እና ፉልሀም ከ ቦርንማውዝ ሌሎች ዛሬ የሚደረጉ ጨዋታዎች ናቸው፡፡
በአንተነህ ሲሳይ
*************
በ36ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬ ምሽት 1 ሰዓት ከ30 ላይ ማንችስተር ሲቲ ብሬንትፎርድን ያስተናግዳል። ከኤቨርተን ጋር ነጥብ መጋራቱን ተከትሎ የሊጉን ዋንጫ የማንሳት ዕድሉ ሙሉ በሙሉ ከእጁ የወጣው ማንችስተር ሲቲ፣ አሁንም ያለውን ጥቂት ዕድል ለመጠቀም እና በአርሰናል ላይ ጫና ለማሳደር ወደ ሜዳ ይገባል።
ሆኖም ዘንድሮ ጠንካራ የውድድር ጊዜ ያሳለፈው ብሬንትፎርድ፣ የአውሮፓ መድረክ ተሳትፎን ለማግኘት እየታገለ በመሆኑ ጨዋታው ለሲቲ እጅግ ፈታኝ እንደሚሆን ይጠበቃል። በተለይ ክሪስታል ፓላስ እና አስቶን ቪላ በዩሮፓ ሊግ እና በኮንፈረንስ ሊግ ለፍጻሜ መድረሳቸውን ተከትሎ፣ በቀጣይ ዓመት በአውሮፓ መድረክ የሚሳተፉ የእንግሊዝ ክለቦች ቁጥር ሊጨምር ስለሚችል በ51 ነጥብ 7ኛ ደረጃ ላይ የተቀመጠው ብሬንትፎርድ ይህንን አጋጣሚ ለመጠቀም ይፋለማል።
በኢትሃድ ስታዲየም በሚደረገው ጨዋታ ሮድሪ ለዛሬው ፍልሚያ ሊደርስ እንደሚችል አሰልጣኝ ፔፕ ጋርዲዮላ ተናግሯል። ጋርዲዮላ ትላንት በሰጠት መግለጫ "በዛሬው ጨዋታ ከተሸነፍን የዋንጫው ጉዞ በይፋ ያበቃል" ሲል የጨዋታውን ወሳኝነት ገልቷል። ሲቲ ካሸነፈ ከአርሰናል ያለውን የነጥብ ልዩነት ወደ ሁለት የሚያጠብ ይሆናል፡፡
ቀን 8 ሰዓት ከ30 ላይ ደግሞ ሊቨርፑል እና ቼልሲ የሚገናኙበት ጨዋታ ይጠበቃል። በፕሪሚየር ሊጉ ያለፉትን ስድስት ተከታታይ ጨዋታዎች የተሸነፈው ቼልሲ፣ ዛሬም በአንፊልድ ሌላ ከባድ ፈተና ይጠብቀዋል። ሊጉ ሊጠናቀቅ ሦስት ጨዋታዎች ብቻ እየቀሩት እስካሁን የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ተሳትፎውን ያላረጋገጠው ሊቨርፑል፣ ከዛሬው ጨዋታ ሦስት ነጥብ ካገኘ መሳተፉን በይፋ የሚያረጋግጥ ይሆናል። በአንፊልድ በሚደረገው ጨዋታ ሞሃመድ ሳላህ እና አሊሰን ቤከር አሁንም በጉዳት ከስብስቡ ውጭ ናቸው። በቼልሲ በኩል ሌቪ ኮልዊል እና ሬስ ጄምስ ለጨዋታው ሊደርሱ ይችላሉ ተብሏል።
በሻምፒዮንስ ሊግ መሳተፉን ቀድሞ ያረጋገጠመው ማንችስተር ዩናይትድ ከ ሜዳው ወጭ ከሰንደርላንድ 11 ሰዓት ላይ ጨዋታውን ያደርጋል፡፡ ብራይተን ከ ዎልቭስ እና ፉልሀም ከ ቦርንማውዝ ሌሎች ዛሬ የሚደረጉ ጨዋታዎች ናቸው፡፡
በአንተነህ ሲሳይ
26 days ago
በሊጉ የዋንጫ ፉክክር ውስጥ ለመቆየትና ላለመውረድ የሚደረጉ ተጠባቂ የሊጉ ጨዋታዎች
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 1፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የ36ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ዛሬ በሚደረጉ አምስት ጨዋታዎች መደረግ ይጀምራል፡፡
ቀን 8 ሰዓት 30 ላይ ሊቨርፑል በሜዳው አንፊልድ ሮድ ቼልሲን የሚያስተናግድበት መርሐ ግብር የዕለቱ ቀዳሚ ጨዋታ ነው፡፡
ሁለቱም ቡድኖች በአውሮፓ መድረክ የሚያሳትፋቸውን ውጤት ይዘው የውድድር ዓመቱን ለማጠናቀቅ እየተፋለሙ ይገኛል፡፡
በሊጉ ከሦስት ተከታታይ ድል በኋላ በሳምንቱ መጨረሻ በማንቼስተር ዩናይትድ ሽንፈት ያስተናገደው ሊቨርፑል ወደ ድል ለመመለስ ወደ ሜዳ ይገባል፡፡
ያለፉትን ስድስት ተከታታይ ጨዋታዎች በሊጉ የተሸነፈው ቼልሲ ወደ ድል ለመምጣት የሚያደርገው ፍልሚያ ይጠበቃል፡፡
ቼልሲ በዛሬው ጨዋታ በሊቨርፑል የሚሸነፍ ከሆነ ከ74 ዓመታት በኋላ ሰባት ተከታታይ የሊግ ጨዋታዎችን የሚሸነፍ ይሆናል፡፡
ሁለቱ ቡድኖች እርስበርስ ካደረጓቸው ያለፉት አምስት ጨዋታዎች ሊቨርፑል በሦስቱ ሲያሸንፍ ቼልሲ በሁለቱ ድል አድርጓል፡፡
አመሻሽ 11 ሰዓት ላይ ማንቼስተር ዩናይትድ ከሜዳው ውጪ ተጉዞ ከሰንደርላንድ ጋር ጨዋታውን ያደርጋል፡፡
የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ተሳትፎውን ያረጋገጠው ማንቼስተር ዩናይትድ በሊጉ አራተኛ ተከታታይ ድሉን ለማሳካት ይፋለማል፡፡
ሰንደርላንድ በበኩሉ ከተከታታይ ሦስት ጨዋታዎች ድል አልባ ጉዞ በኋላ ወደ ድል ለመመለስ ወደ ሜዳ የሚገባ ይሆናል፡፡
ሁለቱ ቡድኖች እርስበርስ ካደረጓቸው ያለፉት አምስት ጨዋታዎች ማንቼስተር ዩናይትድ አራቱን በማሸነፍ የበላይነቱን ሲይዝ ሰንደርላንድ በአንዱ ድል አድርጓል፡፡
በተመሳሳይ ሰዓት ፉልሃም ከቦርንማውዝ እንዲሁም ብራይተን ከወልቭስ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡
ምሽት 1 ሰዓት 30 ላይ ማንቼስተር ሲቲ በሜዳው ኢትሃድ ከብሬንትፎርድ የሚያደርገው ጨዋታ ይጠበቃል፡፡
በ35ኛ ሳምንት የሊጉ መርሐ ግብር ነጥብ የጣለው ማንቼስተር ሲቲ የዋንጫ ፉክክሩን ለማጠናከር ይፋለማል፡፡
ማንቼስተር ሲቲ የዛሬውን ጨዋታ የሚያሸንፍ ከሆነ አርሰናል ነገ ምሽት ጨዋታውን እስከሚያደርግ ድረስ የነጥብ ልዩነቱን ወደ ሁለት ማጥበብ ይችላል፡፡
የሊጉ ጨዋታ ነገ ሲቀጥል የሊጉ መሪ አርሰናል ከሜዳው ውጪ ተጉዞ ምሽት 12 ሰዓት 30 ላይ ከዌስትሃም ዩናይትድ ጋር ይጫወታል፡፡
የሊጉ መሪ አርሰናል መሪነቱን ለማጠናከር እና ዋንጫውን ለማንሳት የሚያደርገውን ጉዞ አጠናክሮ ለመቀጠል ይፋለማል፡፡
ተጋጣሚው ዌስትሃም ዩናይትድ በበኩሉ ላለመውረድ የሚያደርገው ብርቱ ፉክክር ተጠባቂ ነው፡፡
ኖቲንግሃም ፎረስት ከኒውካስል ዩናይትድ፣ ክሪስታል ፓላስ ከኤቨርተን እንዲሁም በርንሌይ ከአስቶንቪላ በዕለቱ በተመሳሳይ ሰዓት ቀን 10 ሰዓት ላይ የሚደረጉ ጨዋታዎች ናቸው፡፡
የ36ኛ ሳምንት የሊጉ መርሐ ግብር ሰኞ ምሽት 4 ሰዓት ላይ ቶተንሃም ሆትስፐር ከሊድስ ዩናይትድ በሚያደርጉት ጨዋታ ይጠናቀቃል፡፡
ሊጉን አርሰናል በ76 ነጥብ ሲመራ ማንቼስተር ሲቲ 71፣ ማንቼስተር ዩናይትድ 64 እንዲሁም ሊቨርፑል በ58 ነጥብ ከ2ኛ እስከ 4ኛ ያለውን ደረጃ ይዘዋል፡፡
ኤርሊንግ ብራውት ሃላንድ በ25 ግቦች የሊጉን ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነት ደረጃ ሲመራ ኢጎር ቲያጎ በ22 ግቦች ይከተላል፡፡
በወንድማገኝ ጸጋዬ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 1፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የ36ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ዛሬ በሚደረጉ አምስት ጨዋታዎች መደረግ ይጀምራል፡፡
ቀን 8 ሰዓት 30 ላይ ሊቨርፑል በሜዳው አንፊልድ ሮድ ቼልሲን የሚያስተናግድበት መርሐ ግብር የዕለቱ ቀዳሚ ጨዋታ ነው፡፡
ሁለቱም ቡድኖች በአውሮፓ መድረክ የሚያሳትፋቸውን ውጤት ይዘው የውድድር ዓመቱን ለማጠናቀቅ እየተፋለሙ ይገኛል፡፡
በሊጉ ከሦስት ተከታታይ ድል በኋላ በሳምንቱ መጨረሻ በማንቼስተር ዩናይትድ ሽንፈት ያስተናገደው ሊቨርፑል ወደ ድል ለመመለስ ወደ ሜዳ ይገባል፡፡
ያለፉትን ስድስት ተከታታይ ጨዋታዎች በሊጉ የተሸነፈው ቼልሲ ወደ ድል ለመምጣት የሚያደርገው ፍልሚያ ይጠበቃል፡፡
ቼልሲ በዛሬው ጨዋታ በሊቨርፑል የሚሸነፍ ከሆነ ከ74 ዓመታት በኋላ ሰባት ተከታታይ የሊግ ጨዋታዎችን የሚሸነፍ ይሆናል፡፡
ሁለቱ ቡድኖች እርስበርስ ካደረጓቸው ያለፉት አምስት ጨዋታዎች ሊቨርፑል በሦስቱ ሲያሸንፍ ቼልሲ በሁለቱ ድል አድርጓል፡፡
አመሻሽ 11 ሰዓት ላይ ማንቼስተር ዩናይትድ ከሜዳው ውጪ ተጉዞ ከሰንደርላንድ ጋር ጨዋታውን ያደርጋል፡፡
የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ተሳትፎውን ያረጋገጠው ማንቼስተር ዩናይትድ በሊጉ አራተኛ ተከታታይ ድሉን ለማሳካት ይፋለማል፡፡
ሰንደርላንድ በበኩሉ ከተከታታይ ሦስት ጨዋታዎች ድል አልባ ጉዞ በኋላ ወደ ድል ለመመለስ ወደ ሜዳ የሚገባ ይሆናል፡፡
ሁለቱ ቡድኖች እርስበርስ ካደረጓቸው ያለፉት አምስት ጨዋታዎች ማንቼስተር ዩናይትድ አራቱን በማሸነፍ የበላይነቱን ሲይዝ ሰንደርላንድ በአንዱ ድል አድርጓል፡፡
በተመሳሳይ ሰዓት ፉልሃም ከቦርንማውዝ እንዲሁም ብራይተን ከወልቭስ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡
ምሽት 1 ሰዓት 30 ላይ ማንቼስተር ሲቲ በሜዳው ኢትሃድ ከብሬንትፎርድ የሚያደርገው ጨዋታ ይጠበቃል፡፡
በ35ኛ ሳምንት የሊጉ መርሐ ግብር ነጥብ የጣለው ማንቼስተር ሲቲ የዋንጫ ፉክክሩን ለማጠናከር ይፋለማል፡፡
ማንቼስተር ሲቲ የዛሬውን ጨዋታ የሚያሸንፍ ከሆነ አርሰናል ነገ ምሽት ጨዋታውን እስከሚያደርግ ድረስ የነጥብ ልዩነቱን ወደ ሁለት ማጥበብ ይችላል፡፡
የሊጉ ጨዋታ ነገ ሲቀጥል የሊጉ መሪ አርሰናል ከሜዳው ውጪ ተጉዞ ምሽት 12 ሰዓት 30 ላይ ከዌስትሃም ዩናይትድ ጋር ይጫወታል፡፡
የሊጉ መሪ አርሰናል መሪነቱን ለማጠናከር እና ዋንጫውን ለማንሳት የሚያደርገውን ጉዞ አጠናክሮ ለመቀጠል ይፋለማል፡፡
ተጋጣሚው ዌስትሃም ዩናይትድ በበኩሉ ላለመውረድ የሚያደርገው ብርቱ ፉክክር ተጠባቂ ነው፡፡
ኖቲንግሃም ፎረስት ከኒውካስል ዩናይትድ፣ ክሪስታል ፓላስ ከኤቨርተን እንዲሁም በርንሌይ ከአስቶንቪላ በዕለቱ በተመሳሳይ ሰዓት ቀን 10 ሰዓት ላይ የሚደረጉ ጨዋታዎች ናቸው፡፡
የ36ኛ ሳምንት የሊጉ መርሐ ግብር ሰኞ ምሽት 4 ሰዓት ላይ ቶተንሃም ሆትስፐር ከሊድስ ዩናይትድ በሚያደርጉት ጨዋታ ይጠናቀቃል፡፡
ሊጉን አርሰናል በ76 ነጥብ ሲመራ ማንቼስተር ሲቲ 71፣ ማንቼስተር ዩናይትድ 64 እንዲሁም ሊቨርፑል በ58 ነጥብ ከ2ኛ እስከ 4ኛ ያለውን ደረጃ ይዘዋል፡፡
ኤርሊንግ ብራውት ሃላንድ በ25 ግቦች የሊጉን ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነት ደረጃ ሲመራ ኢጎር ቲያጎ በ22 ግቦች ይከተላል፡፡
በወንድማገኝ ጸጋዬ
29 days ago
ኮቢ ማይኖ በፕሪሚየር ሊጉ የሳምንቱ ኮከብ ነው ተባለ
#ethiopia | የማንችስተር ዩናይትዱ የዝግጅት ክፍል ውጤት የሆነው ወጣቱ ድንቅ ታላንት ኮቢ ማይኖ፣ በ35ኛው ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የሳምንቱ ምርጥ ተጨዋች ተብሎ ተመርጧል።
ማይኖ በተለይ በታሪካዊው ተቀናቃኝ ሊቨርፑል ላይ ያስቆጠራት ያቺ አስደናቂ የማሸነፊያ ግብ፣ ለዚህ ክብር ለመታጨትና ሽልማቱን ለመውሰድ ዋነኛ ምክንያት ሆናለታል።
እድሜው ገና ወጣት ቢሆንም፣ በሜዳ ላይ የሚያሳየው መረጋጋትና ብስለት የብዙዎችን ቀልብ መሳቡን ቀጥሏል።
ምንም እንኳን የቡድኑ የውድድር ዘመን ጉዞ ውጣ ውረድ የበዛበት ቢሆንም፣ የተጨዋቾቹ የግል ብቃት ግን እጅግ አስደናቂ ነው። ዘንድሮ የክለቡ ተጨዋቾች የሳምንቱን ምርጥ ተጨዋች ሽልማት የግላቸው በማድረግ ረገድ ወደር አልተገኘላቸውም፦
13/36፡ በዘንድሮው የውድድር ዘመን እስካሁን ከተሰጡት 36 የሳምንቱ ምርጥ ተጨዋች ሽልማቶች መካከል 13ቱን የወሰዱት የኦልድትራፎርድ ተጨዋቾች ናቸው።
ይህም ማለት በሊጉ ካሉት የሳምንቱ ኮከብ ሽልማቶች ውስጥ 36% የሚሆነውን ማንችስተር ዩናይትድ ጠቅልሎ ወስዷል ማለት ነው።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#kobbiemainoo #mufc #premierleague #manunited #ethiopia #footballnews #የሳምንቱ_ኮከብ
#ethiopia | የማንችስተር ዩናይትዱ የዝግጅት ክፍል ውጤት የሆነው ወጣቱ ድንቅ ታላንት ኮቢ ማይኖ፣ በ35ኛው ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የሳምንቱ ምርጥ ተጨዋች ተብሎ ተመርጧል።
ማይኖ በተለይ በታሪካዊው ተቀናቃኝ ሊቨርፑል ላይ ያስቆጠራት ያቺ አስደናቂ የማሸነፊያ ግብ፣ ለዚህ ክብር ለመታጨትና ሽልማቱን ለመውሰድ ዋነኛ ምክንያት ሆናለታል።
እድሜው ገና ወጣት ቢሆንም፣ በሜዳ ላይ የሚያሳየው መረጋጋትና ብስለት የብዙዎችን ቀልብ መሳቡን ቀጥሏል።
ምንም እንኳን የቡድኑ የውድድር ዘመን ጉዞ ውጣ ውረድ የበዛበት ቢሆንም፣ የተጨዋቾቹ የግል ብቃት ግን እጅግ አስደናቂ ነው። ዘንድሮ የክለቡ ተጨዋቾች የሳምንቱን ምርጥ ተጨዋች ሽልማት የግላቸው በማድረግ ረገድ ወደር አልተገኘላቸውም፦
13/36፡ በዘንድሮው የውድድር ዘመን እስካሁን ከተሰጡት 36 የሳምንቱ ምርጥ ተጨዋች ሽልማቶች መካከል 13ቱን የወሰዱት የኦልድትራፎርድ ተጨዋቾች ናቸው።
ይህም ማለት በሊጉ ካሉት የሳምንቱ ኮከብ ሽልማቶች ውስጥ 36% የሚሆነውን ማንችስተር ዩናይትድ ጠቅልሎ ወስዷል ማለት ነው።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#kobbiemainoo #mufc #premierleague #manunited #ethiopia #footballnews #የሳምንቱ_ኮከብ
29 days ago
የባቫሪያኑ ፊት አውራሪዎች…
አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 28፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የባየርን ሙኒክ የፊት መስመር ተጣማሪዎቹ ሀሪ ኬን፣ ሉዊስ ዲያዝ እና ማይክል ኦሊሴ በሀገር ውስጥ ውድድሮችና በአውሮፓ መድረክ አስደናቂ ጉዞ እያደረጉ ይገኛሉ፡፡
ይህ የባቫሪያኑ ጥምረት በዚህ የውድድር ዓመት ያስቆጠራቸው ግቦች 100 የደረሱ ሲሆን÷ የሪያል ማድሪዶቹ ኪሊያን ምባፔ፣ ቪኒ ጁኒየር እና ቫልቬርዴ በ71 ግቦች በሁለተኛነት ይከተላሉ፡፡
በቪንሴንት ኮምፓኒ የሚመራው ባየርን ሙኒክ በቡንደስሊጋው ብቻ እስካሁን 116 ግቦችን (በአማካይ በአንድ ጨዋታ ከሦስት በላይ ግቦችን) ያስቆጠረ ሲሆን፥ አራት ጨዋታዎች እየቀሩት የሊጉ ሻምፒዮን መሆኑ ይታወቃል፡፡
በአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ግማሽ ፍጻሜ ላይ የሚገኘው የጀርመኑ ክለብ በአስፈሪ የማጥቃት እንቅስቃሴ ለተጋጣሚዎቹ የተከላካይ መስመር ፈተና ሆኖ ቀጥሏል፡፡
በውድድሩ በዚህ ዓመት እስካሁን ባደረጋቸው 13 ጨዋታዎች በኬን፣ ዲያዝና ኦሊሴ የሚመራው የባቫሪያኑ የፊት መስመር በተጋጣሚዎቹ ላይ 41 ግቦችን አስቆጥሯል፡፡
ባየርን ሙኒክ ባለፈው ሳምንት በመድረኩ በፒኤስጂ 5 ለ 4 በተሸነፈበት የግማሽ ፍጻሜው የመጀመሪያ ዙር ጨዋታ ሦስቱም ተጫዋቾች ግብ ማስቆጠራቸው ይታወሳል፡፡
በሁሉም ውድድሮች በጋራ በዚህ የውድድር ዓመት ብቻ እስካሁን 100 ግቦችን ያስቆጠሩ ሲሆን፥ ከዚህ ውስጥ 54ቱ ግቦች በእንግሊዛዊው ኮከብ ሀሪ ኬን የተቆጠሩ ናቸው፡፡
ባለፈው ክረምት በ75 ሚሊየን ዩሮ የዝውውር ሂሳብ ሊቨርፑልን ለቅቆ ወደ ባየርን ሙኒክ ያቀናው ኮሎምቢያዊው ኮከብ ሉዊስ ዲያዝ 26 ግቦችን ከመረብ አሳርፏል፡፡
20 ጊዜ ኳስና መረብን ያገናኘው ፈረንሳዊው ኮከብ ማይክል ኦሊሴ ከቀኝ መስመር እየተነሳ ከሚያስቆጥራቸው ግቦች በተጨማሪ ያለቀላቸውን ኳሶች አመቻችቶ በማቀበል ወሳኝ ተጫዋች መሆኑን እያስመለከተ ይገኛል፡፡
ይህ የባየርን ሙኒክ የፊት መስመር ጥምረት ከአስር ዓመታት ወዲህ በአንድ የውድድር ዓመት 100 እና ከዚያ በላይ ግቦች በማስቆጠር ሦስተኛው ጥምረት ሆኗል፡፡
ከዚህ ቀደም በፈረንጆቹ 2015/16 የውድድር ዓመት ሊዮኔል ሜሲ፣ ሉዊስ ሱዋሬዝ እና ኔይማር በባርሴሎና 131 እንዲሁም ክርስቲያኖ ሮናልዶ፣ ካሪም ቤንዜማ እና ጋሪዝ ቤል በሪያል ማድሪድ በጋራ 100 ግቦችን ማስቆጠር ችለዋል፡፡
ሙኒክ በሻምፒየንስ ሊግ ለ7ኛ ጊዜ ሻምፒዮንነትን እያለመ ወደ ፍጻሜው ለመሻገር በሚያደርገው ጉዞ በዛሬ ምሽቱ የግማሽ ፍጻሜ የመልስ ጨዋታ የሦስቱ ተጫዋቾች ሚና ከወዲሁ ይጠበቃል፡፡
በኃይለማርያም ተገኝ
አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 28፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የባየርን ሙኒክ የፊት መስመር ተጣማሪዎቹ ሀሪ ኬን፣ ሉዊስ ዲያዝ እና ማይክል ኦሊሴ በሀገር ውስጥ ውድድሮችና በአውሮፓ መድረክ አስደናቂ ጉዞ እያደረጉ ይገኛሉ፡፡
ይህ የባቫሪያኑ ጥምረት በዚህ የውድድር ዓመት ያስቆጠራቸው ግቦች 100 የደረሱ ሲሆን÷ የሪያል ማድሪዶቹ ኪሊያን ምባፔ፣ ቪኒ ጁኒየር እና ቫልቬርዴ በ71 ግቦች በሁለተኛነት ይከተላሉ፡፡
በቪንሴንት ኮምፓኒ የሚመራው ባየርን ሙኒክ በቡንደስሊጋው ብቻ እስካሁን 116 ግቦችን (በአማካይ በአንድ ጨዋታ ከሦስት በላይ ግቦችን) ያስቆጠረ ሲሆን፥ አራት ጨዋታዎች እየቀሩት የሊጉ ሻምፒዮን መሆኑ ይታወቃል፡፡
በአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ግማሽ ፍጻሜ ላይ የሚገኘው የጀርመኑ ክለብ በአስፈሪ የማጥቃት እንቅስቃሴ ለተጋጣሚዎቹ የተከላካይ መስመር ፈተና ሆኖ ቀጥሏል፡፡
በውድድሩ በዚህ ዓመት እስካሁን ባደረጋቸው 13 ጨዋታዎች በኬን፣ ዲያዝና ኦሊሴ የሚመራው የባቫሪያኑ የፊት መስመር በተጋጣሚዎቹ ላይ 41 ግቦችን አስቆጥሯል፡፡
ባየርን ሙኒክ ባለፈው ሳምንት በመድረኩ በፒኤስጂ 5 ለ 4 በተሸነፈበት የግማሽ ፍጻሜው የመጀመሪያ ዙር ጨዋታ ሦስቱም ተጫዋቾች ግብ ማስቆጠራቸው ይታወሳል፡፡
በሁሉም ውድድሮች በጋራ በዚህ የውድድር ዓመት ብቻ እስካሁን 100 ግቦችን ያስቆጠሩ ሲሆን፥ ከዚህ ውስጥ 54ቱ ግቦች በእንግሊዛዊው ኮከብ ሀሪ ኬን የተቆጠሩ ናቸው፡፡
ባለፈው ክረምት በ75 ሚሊየን ዩሮ የዝውውር ሂሳብ ሊቨርፑልን ለቅቆ ወደ ባየርን ሙኒክ ያቀናው ኮሎምቢያዊው ኮከብ ሉዊስ ዲያዝ 26 ግቦችን ከመረብ አሳርፏል፡፡
20 ጊዜ ኳስና መረብን ያገናኘው ፈረንሳዊው ኮከብ ማይክል ኦሊሴ ከቀኝ መስመር እየተነሳ ከሚያስቆጥራቸው ግቦች በተጨማሪ ያለቀላቸውን ኳሶች አመቻችቶ በማቀበል ወሳኝ ተጫዋች መሆኑን እያስመለከተ ይገኛል፡፡
ይህ የባየርን ሙኒክ የፊት መስመር ጥምረት ከአስር ዓመታት ወዲህ በአንድ የውድድር ዓመት 100 እና ከዚያ በላይ ግቦች በማስቆጠር ሦስተኛው ጥምረት ሆኗል፡፡
ከዚህ ቀደም በፈረንጆቹ 2015/16 የውድድር ዓመት ሊዮኔል ሜሲ፣ ሉዊስ ሱዋሬዝ እና ኔይማር በባርሴሎና 131 እንዲሁም ክርስቲያኖ ሮናልዶ፣ ካሪም ቤንዜማ እና ጋሪዝ ቤል በሪያል ማድሪድ በጋራ 100 ግቦችን ማስቆጠር ችለዋል፡፡
ሙኒክ በሻምፒየንስ ሊግ ለ7ኛ ጊዜ ሻምፒዮንነትን እያለመ ወደ ፍጻሜው ለመሻገር በሚያደርገው ጉዞ በዛሬ ምሽቱ የግማሽ ፍጻሜ የመልስ ጨዋታ የሦስቱ ተጫዋቾች ሚና ከወዲሁ ይጠበቃል፡፡
በኃይለማርያም ተገኝ
1 month ago
"ያገኟት አንዲት ነጥብ በውድድር ዓመቱ መጨረሻ ላይ ምን ያህል ወሳኝ እንደምትሆን አናውቅም፤ ነገር ግን ሁሉም አካል በውጤቱ ቅር የተሰኘ ይመስላል። ማንችስተር ሲቲዎች 1 ለ 0 ይመሩ ስለነበር ቅር መሰኘታቸው አይቀርም። የአርሰናል ዋነኛ ተቀናቃኝ የሆኑት ሲቲዎች ሁለት ነጥቦችን ቢጥሉም፣ የአርሰናል ተጫዋቾች እና ደጋፊዎች ግን (ሲቲ) ሙሉ በሙሉ ሊሸነፍ የሚችልበት አጋጣሚ በማምለጡ እጅግ ማዘናቸው አይቀርም። ምን ዓይነት ጨዋታ ነው! የማይታመን ነው።"
ጄሚ ካራገር
(የቀድሞው የሊቨርፑል ተከላካይ በስካይ ስፖርት ላይ የሰጠው አስተያየት)
ጄሚ ካራገር
(የቀድሞው የሊቨርፑል ተከላካይ በስካይ ስፖርት ላይ የሰጠው አስተያየት)
1 month ago
ማንችስተር ዩናይትድ ከ ሊቨርፑል
************
በ35ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ፣ ዛሬ 11 ሰዓት ከ30 ላይ ማንችስተር ዩናይትድ እና ሊቨርፑል የሚያደርጉት ጨዋታ ይጠበቃል። ትላንት በተደረገው ጨዋታ ብራይተን በኒውካስትል ዩናይትድ መሸነፉን ተከትሎ የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ተሳትፎውን ያረጋገጠው ማንችስተር ዩናይትድ የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ተሳትፎውን ለማረጋገጥ ከሚታገለው ሊቨርፑል ይጫወታል፡፡
ከዩናይትድ በሦስት ነጥብ ዝቅ ብሎ በ58 ነጥብ 4ኛ ደረጃ ላይ የተቀመጠው የመርሲሳይዱ ክለብ፣ የዛሬውን ጨዋታ ካሸነፈ የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ተሳትፎውን በይፋ የሚያረጋግጥ ይሆናል። ዩናይትድ ከሊቨርፑል ጋር በተገናኘባቸው ያለፉት 19 የፕሪሚየር ሊግ ጨዋታዎች ማሸነፍ የቻለው ሦስቱን ብቻ ሲሆን፣ በኦልድ ትራፎርድ ባደረጋቸው ያለፉት አምስት ጨዋታዎችም በሦስቱ ተሸንፏል፡፡
ማይክል ካሪክ ሩብን አሞሪምን ተክቶ ወደ ኦልድ ትራፎርድ ከመጣ በኋላ፣ እንደ እሱ ብዙ ነጥብ የሰበሰበ አሰልጣኝ በሊጉ የለም። ለዛሬው ጨዋታ ማቲያስ ኩኛ ከጉዳቱ በማገገሙ ሊሰለፍ ይችላል ተብሎ የሚጠበቅ ሲሆን፣ ሉክ ሾውም በተመሳሳይ ወደ ሜዳ ሊመለስ ይችላል። ሆኖም ማቲያስ ዴሊክት ልምምድ ቢጀምርም በዛሬው ስብስብ ውስጥ እንዳልተካተተ ማይክል ካሪክ አረጋግጠዋል።
በሊቨርፑል በኩል በርካታ የጉዳት ያሉ ሲሆን ግብ ጠባቂዎቹ አሊሰን ቤከር እና ጆርጂ ማማርዳሽቪል በጉዳት ከቡድኑ ውጭ በመሆናቸው፣ ሦስተኛው ግብ ጠባቂ ፍሬዲ ውድማን በቋሚነት የሚሰለፍ ይሆናል። በተጨማሪም ሞሃመድ ሳላህ፣ ሁጎ ኢኪቲኬ እና ኮኖር ብራድሊ በጉዳት ምክንያት ከዛሬው ስብስብ ውጭ ናቸው። ሁለቱ ክለቦች ዛሬ ለ244ኛ ጊዜ ይገናኛሉ፡፡
በሊጉ ለመቆየት እየታገለ የሚገኘው ቶተንሀም ሆትስፐር ምሽት 3 ሰዓት ላይ ከሜዳው ውጭ ከአስቶን ቪላ ጋር ይጫወታል። በ34 ነጥብ ወራጅ ቀጠና ውስጥ የሚገኘው የሰሜን ለንደኑ ክለብ፣ የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ተሳትፎን ለማግኘት ከሚታገለው አስቶን ቪላ ሌላ ከባድ ፈተና ይጠብቀዋል።
ዌስትሃም ትላንት በብሬንትፎርድ መሸነፉን ተከትሎ፣ ቶተንሃም ዛሬ ካሸነፈ ከወራጅ ቀጠናው የመውጣት ዕድል ይኖረዋል። ሆኖም ስፐርስ ዛሬም እንደ ሞሃመድ ኩዱስ፣ ቤን ዴቪስ፣ ቪካሪዮ እና ክርስቲያን ሮሜሮ ያሉ ወሳኝ ተጫዋቾችን በጉዳት ምክንያት የማይጠቀም ይሆናል። በተጨማሪም 10 ሰዓት ላይ ቦርንማውዝ ከክሪስታል ፓላስ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ።
በአንተነህ ሲሳይ
#ethiopiabroadcastingcorporation #epl #manchesterunited #liverpool
************
በ35ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ፣ ዛሬ 11 ሰዓት ከ30 ላይ ማንችስተር ዩናይትድ እና ሊቨርፑል የሚያደርጉት ጨዋታ ይጠበቃል። ትላንት በተደረገው ጨዋታ ብራይተን በኒውካስትል ዩናይትድ መሸነፉን ተከትሎ የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ተሳትፎውን ያረጋገጠው ማንችስተር ዩናይትድ የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ተሳትፎውን ለማረጋገጥ ከሚታገለው ሊቨርፑል ይጫወታል፡፡
ከዩናይትድ በሦስት ነጥብ ዝቅ ብሎ በ58 ነጥብ 4ኛ ደረጃ ላይ የተቀመጠው የመርሲሳይዱ ክለብ፣ የዛሬውን ጨዋታ ካሸነፈ የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ተሳትፎውን በይፋ የሚያረጋግጥ ይሆናል። ዩናይትድ ከሊቨርፑል ጋር በተገናኘባቸው ያለፉት 19 የፕሪሚየር ሊግ ጨዋታዎች ማሸነፍ የቻለው ሦስቱን ብቻ ሲሆን፣ በኦልድ ትራፎርድ ባደረጋቸው ያለፉት አምስት ጨዋታዎችም በሦስቱ ተሸንፏል፡፡
ማይክል ካሪክ ሩብን አሞሪምን ተክቶ ወደ ኦልድ ትራፎርድ ከመጣ በኋላ፣ እንደ እሱ ብዙ ነጥብ የሰበሰበ አሰልጣኝ በሊጉ የለም። ለዛሬው ጨዋታ ማቲያስ ኩኛ ከጉዳቱ በማገገሙ ሊሰለፍ ይችላል ተብሎ የሚጠበቅ ሲሆን፣ ሉክ ሾውም በተመሳሳይ ወደ ሜዳ ሊመለስ ይችላል። ሆኖም ማቲያስ ዴሊክት ልምምድ ቢጀምርም በዛሬው ስብስብ ውስጥ እንዳልተካተተ ማይክል ካሪክ አረጋግጠዋል።
በሊቨርፑል በኩል በርካታ የጉዳት ያሉ ሲሆን ግብ ጠባቂዎቹ አሊሰን ቤከር እና ጆርጂ ማማርዳሽቪል በጉዳት ከቡድኑ ውጭ በመሆናቸው፣ ሦስተኛው ግብ ጠባቂ ፍሬዲ ውድማን በቋሚነት የሚሰለፍ ይሆናል። በተጨማሪም ሞሃመድ ሳላህ፣ ሁጎ ኢኪቲኬ እና ኮኖር ብራድሊ በጉዳት ምክንያት ከዛሬው ስብስብ ውጭ ናቸው። ሁለቱ ክለቦች ዛሬ ለ244ኛ ጊዜ ይገናኛሉ፡፡
በሊጉ ለመቆየት እየታገለ የሚገኘው ቶተንሀም ሆትስፐር ምሽት 3 ሰዓት ላይ ከሜዳው ውጭ ከአስቶን ቪላ ጋር ይጫወታል። በ34 ነጥብ ወራጅ ቀጠና ውስጥ የሚገኘው የሰሜን ለንደኑ ክለብ፣ የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ተሳትፎን ለማግኘት ከሚታገለው አስቶን ቪላ ሌላ ከባድ ፈተና ይጠብቀዋል።
ዌስትሃም ትላንት በብሬንትፎርድ መሸነፉን ተከትሎ፣ ቶተንሃም ዛሬ ካሸነፈ ከወራጅ ቀጠናው የመውጣት ዕድል ይኖረዋል። ሆኖም ስፐርስ ዛሬም እንደ ሞሃመድ ኩዱስ፣ ቤን ዴቪስ፣ ቪካሪዮ እና ክርስቲያን ሮሜሮ ያሉ ወሳኝ ተጫዋቾችን በጉዳት ምክንያት የማይጠቀም ይሆናል። በተጨማሪም 10 ሰዓት ላይ ቦርንማውዝ ከክሪስታል ፓላስ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ።
በአንተነህ ሲሳይ
#ethiopiabroadcastingcorporation #epl #manchesterunited #liverpool
Sponsored by
Surafel
1 month ago
(ዘ-ሐበሻ ስፖርት) በክረምቱ የዝውውር መስኮት ዋና አሰልጣኙን ቶማስ ፍራንክን፣ አንበሉን ክርስቲያን ኖርጋርድን እና ኮከብ አጥቂውን ብራያን ምቡዌሞን ያጣው ብሬንትፎርድ፣ ዘንድሮ ከፕሪሚየር ሊጉ ይወርዳል ብሎ ያልገመተ የኳስ አፍቃሪ አልነበረም። ነገር ግን በምትካቸው የመጡት አዲሱ አሰልጣኝ ኪዝ አንድሪውስ፣ እንዲሁም ተጫዋቾቹ ኢጎር ቲያጎ እና ዳንጎ ኦዋታራ ይህንን ግምት ሙሉ በሙሉ ገልብጠውታል።
"ንቦቹ" በክለቡ ታሪክ እጅግ አስደናቂ ከሚባሉት የውድድር ዓመታት ውስጥ አንዱን እያሳለፉ ይገኛሉ። ሊጉ ሊጠናቀቅ ሶስት ጨዋታዎች ብቻ በቀሩበት በአሁኑ ሰዓት፣ ብሬንትፎርድ በደረጃ ሰንጠረዡ ስድስተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጦ የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ተሳትፎን እያለመ ነው። ከመጀመሪያ እስከ አምስተኛ ያለው ደረጃ የተረጋገጠ ቢመስልም፣ ከብሬንትፎርድ እስከ 12ኛ ባለው ስፍራ ላይ ባሉ ክለቦች (ሰንደርላንድን ጨምሮ) መካከል ያለው የነጥብ ልዩነት አራት ብቻ መሆኑ ቀሪዎቹን የሊጉን ሳምንታት እጅግ ልብ አንጠልጣይ ያደርጋቸዋል።
ብሬንትፎርድ ወይም ስድስተኛ ሆኖ የሚያጠናቅቀው ሌላ ክለብ፣ ከዩሮፓ ሊግ ባለፈ የሻምፒዮንስ ሊግ ትኬትን ሊቆርጥ የሚችልበት አስገራሚ ቀመር አለ። የፕሪሚየር ሊጉ አምስት ክለቦችን በሻምፒዮንስ ሊግ ማሳተፍ መቻሉን ተከትሎ፣ አስቶን ቪላ የዩሮፓ ሊግን ዋንጫ አንስቶ በፕሪሚየር ሊጉ ደግሞ አምስተኛ ሆኖ ካጠናቀቀ፣ ስድስተኛው ደረጃ በቀጥታ የሻምፒዮንስ ሊግ ተሳትፎን ያረጋግጣል። ነገር ግን አስቶን ቪላ በሊጉ ከአንድ እስከ አራት ባለው ደረጃ ውስጥ ከገባ፣ ይህ እድል ለአውሮፓ ሊግ ሻምፒዮኑ ሳይሆን ከፍተኛ የዩኤፋ ኮፊሸንት ላለው ሌላ ክለብ (ለምሳሌ ለስኮትላንዱ ሬንጀርስ) ይሰጣል። ስለዚህ የብሬንትፎርድ ደጋፊዎች ሐሙስ ዕለት አስቶን ቪላ ኖቲንግሃም ፎረስትን የሚያስተናግድበትን የዩሮፓ ሊግ ግማሽ ፍፃሜ የመልስ ጨዋታ በጉጉት እና በፀሎት ይጠብቃሉ።
በዘንድሮው የውድድር ዓመት ለመጀመሪያ ጊዜ የዋና አሰልጣኝነት ሚናን የተረከቡት ኪዝ አንድሪውስ፣ በወቅታዊ አቋማቸው ዙሪያ ሲናገሩ "ፉክክሩ እጅግ ጠባብ ነው። እስካሁን የተለየ እና ድንቅ ጊዜ አሳልፈናል፤ ይህንኑ ማስቀጠል እንፈልጋለን፤ ወደፊት መግፋታችንን አናቆምም" በማለት ጠንካራ የድል ስነ-ልቦናቸውን አሳይተዋል።
ይሁን እንጂ የብሬንትፎርድ ቀሪ ጉዞ ፈተና የበዛበት ነው። በቀጣይ ማንቸስተር ሲቲን፣ ክሪስታል ፓላስን እና ሊቨርፑልን የሚገጥም ሲሆን፤ ተከታዮቹ ብራይተን (በአንድ ነጥብ ዝቅ ብሎ)፣ ቦርንማውዝ (በሁለት ነጥብ ዝቅ ብሎ እና አንድ ተስተካካይ ጨዋታ ይዞ) እንዲሁም ቼልሲ (በሶስት ነጥብ ዝቅ ብሎ እና አንድ ጨዋታ እየቀረው) ስድስተኛውን ደረጃ ለመንጠቅ አሰፍስፈዋል። ከዚህም ባለፈ በ13ኛ ደረጃ ላይ የሚገኘው የኒውካስሉ አንበል ብሩኖ ጊማሬስ ሳይቀር ቡድኑ ብራይተንን 3-1 ካሸነፈ በኋላ "አሁንም የአውሮፓ ተሳትፎ ተስፋ አለን፤ ቀሪዎቹን ጨዋታዎች ማሸነፍ አለብን" በማለት ፉክክሩን ይበልጥ አግሎታል። በአጠቃላይ እስከ ዘጠኝ የሚደርሱ የእንግሊዝ ክለቦች በሚቀጥለው ዓመት በአውሮፓ መድረክ ሊሳተፉ የሚችሉበት ሰፊ እድል የተፈጠረ ሲሆን፣ የዘንድሮው የፕሪሚየር ሊግ ፍጻሜም የሞት ሽረት ትግል የሚታይበት እንደሚሆን ይጠበቃል።
"ንቦቹ" በክለቡ ታሪክ እጅግ አስደናቂ ከሚባሉት የውድድር ዓመታት ውስጥ አንዱን እያሳለፉ ይገኛሉ። ሊጉ ሊጠናቀቅ ሶስት ጨዋታዎች ብቻ በቀሩበት በአሁኑ ሰዓት፣ ብሬንትፎርድ በደረጃ ሰንጠረዡ ስድስተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጦ የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ተሳትፎን እያለመ ነው። ከመጀመሪያ እስከ አምስተኛ ያለው ደረጃ የተረጋገጠ ቢመስልም፣ ከብሬንትፎርድ እስከ 12ኛ ባለው ስፍራ ላይ ባሉ ክለቦች (ሰንደርላንድን ጨምሮ) መካከል ያለው የነጥብ ልዩነት አራት ብቻ መሆኑ ቀሪዎቹን የሊጉን ሳምንታት እጅግ ልብ አንጠልጣይ ያደርጋቸዋል።
ብሬንትፎርድ ወይም ስድስተኛ ሆኖ የሚያጠናቅቀው ሌላ ክለብ፣ ከዩሮፓ ሊግ ባለፈ የሻምፒዮንስ ሊግ ትኬትን ሊቆርጥ የሚችልበት አስገራሚ ቀመር አለ። የፕሪሚየር ሊጉ አምስት ክለቦችን በሻምፒዮንስ ሊግ ማሳተፍ መቻሉን ተከትሎ፣ አስቶን ቪላ የዩሮፓ ሊግን ዋንጫ አንስቶ በፕሪሚየር ሊጉ ደግሞ አምስተኛ ሆኖ ካጠናቀቀ፣ ስድስተኛው ደረጃ በቀጥታ የሻምፒዮንስ ሊግ ተሳትፎን ያረጋግጣል። ነገር ግን አስቶን ቪላ በሊጉ ከአንድ እስከ አራት ባለው ደረጃ ውስጥ ከገባ፣ ይህ እድል ለአውሮፓ ሊግ ሻምፒዮኑ ሳይሆን ከፍተኛ የዩኤፋ ኮፊሸንት ላለው ሌላ ክለብ (ለምሳሌ ለስኮትላንዱ ሬንጀርስ) ይሰጣል። ስለዚህ የብሬንትፎርድ ደጋፊዎች ሐሙስ ዕለት አስቶን ቪላ ኖቲንግሃም ፎረስትን የሚያስተናግድበትን የዩሮፓ ሊግ ግማሽ ፍፃሜ የመልስ ጨዋታ በጉጉት እና በፀሎት ይጠብቃሉ።
በዘንድሮው የውድድር ዓመት ለመጀመሪያ ጊዜ የዋና አሰልጣኝነት ሚናን የተረከቡት ኪዝ አንድሪውስ፣ በወቅታዊ አቋማቸው ዙሪያ ሲናገሩ "ፉክክሩ እጅግ ጠባብ ነው። እስካሁን የተለየ እና ድንቅ ጊዜ አሳልፈናል፤ ይህንኑ ማስቀጠል እንፈልጋለን፤ ወደፊት መግፋታችንን አናቆምም" በማለት ጠንካራ የድል ስነ-ልቦናቸውን አሳይተዋል።
ይሁን እንጂ የብሬንትፎርድ ቀሪ ጉዞ ፈተና የበዛበት ነው። በቀጣይ ማንቸስተር ሲቲን፣ ክሪስታል ፓላስን እና ሊቨርፑልን የሚገጥም ሲሆን፤ ተከታዮቹ ብራይተን (በአንድ ነጥብ ዝቅ ብሎ)፣ ቦርንማውዝ (በሁለት ነጥብ ዝቅ ብሎ እና አንድ ተስተካካይ ጨዋታ ይዞ) እንዲሁም ቼልሲ (በሶስት ነጥብ ዝቅ ብሎ እና አንድ ጨዋታ እየቀረው) ስድስተኛውን ደረጃ ለመንጠቅ አሰፍስፈዋል። ከዚህም ባለፈ በ13ኛ ደረጃ ላይ የሚገኘው የኒውካስሉ አንበል ብሩኖ ጊማሬስ ሳይቀር ቡድኑ ብራይተንን 3-1 ካሸነፈ በኋላ "አሁንም የአውሮፓ ተሳትፎ ተስፋ አለን፤ ቀሪዎቹን ጨዋታዎች ማሸነፍ አለብን" በማለት ፉክክሩን ይበልጥ አግሎታል። በአጠቃላይ እስከ ዘጠኝ የሚደርሱ የእንግሊዝ ክለቦች በሚቀጥለው ዓመት በአውሮፓ መድረክ ሊሳተፉ የሚችሉበት ሰፊ እድል የተፈጠረ ሲሆን፣ የዘንድሮው የፕሪሚየር ሊግ ፍጻሜም የሞት ሽረት ትግል የሚታይበት እንደሚሆን ይጠበቃል።
1 month ago
አርሰናል ከተከታዩ ማንቼስተር ሲቲ በ6 ነጥብ ለመራቅ
አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 24፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ35ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር አርሰናል በሜዳው ኢምሬትስ ምሽት 1 ሰዓት 30 ላይ ፉልሃምን ያስተናግዳል፡፡
ሊጉን ከተከታዩ ማንቼስተር ሲቲ በሦስት ነጥብ ልዩነት እየመራ የሚገኘው አርሰናል ከዚህ በኋላ የሚያደርጋቸው ጨዋታዎች ለዋንጫው በሚያደርገው ጉዞ ውስጥ ወሳኝ ናቸው፡፡
የካራባኦ ካፕ ዋንጫ ያጣውና ከኤፍ ኤ ውድድር የተሰናበተው አርሰናል በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ እና በአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ዋንጫውን ለማንሳት የሚያደርገው ጉዞ ይጠበቃል፡፡
በሊጉ ከተከታታይ ሁለት ጨዋታዎች ሽንፈት በኋላ ባሳለፍነው ሳምንት ኒውካስል ዩናይትድን በማሸነፍ ወደ ድል የተመለሰው አርሰናል ተከታታይ ጨዋታ በሊጉ ድል ለማድረግ ወደ ሜዳ የሚገባ ይሆናል፡፡
ተጋጣሚው ፉልሃም ከሁለት ተከታታይ ጨዋታዎች ድል አልባ ጉዞ በኋላ ባሳለፍነው ሳምንት ወደ ድል የተመለሰ ሲሆን አሸናፊነቱን ለማስቀጠል ብርቱ ፉክክር ያደርጋል ተብሎ ይጠበቃል፡፡
ሁለቱ ቡድኖች እርስ በርስ ካደረጓቸው ያለፉት አምስት ጨዋታዎች አርሰናል በሁለቱ ሲያሸንፍ፥ ፉልሃም በአንዱ ድል አድርጎ በቀሪ ሁለት ጨዋታዎች ደግሞ አቻ ተለያይተዋል፡፡
አርሰናል የዛሬ ምሽቱን ጨዋታ የሚያሸንፍ ከሆነ ማንቼስተር ሲቲ ሰኞ ምሽት ጨዋታውን እስከሚያደርግ ድረስ የነጥብ ልዩነቱን ወደ ስድስት ከፍ ማድረግ ይችላል፡፡
መውረዱን አስቀድሞ ያረጋገጠው ወልቭስ ከሰንደርላንድ፣ ኒውካስል ዩናይትድ ከብራይተን እንዲሁም ብሬንትፎርድ ከዌስትሃም ዩናይትድ በተመሳሳይ አመሻሽ 11 ሰዓት ላይ የሚደረጉ የዛሬ ጨዋታዎች ናቸው፡፡
ነገ የሊጉ ጨዋታ ሲቀጥል ማንቼስተር ዩናይትድ በሜዳው ኦልድትራፎርድ አመሻሽ 11 ሰዓት 30 ላይ ሊቨርፑልን ያስተናግዳል፡፡
ሁለቱም ቡድኖች የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ተሳትፎ ቦታን ለማግኘት እየተፋለሙ ይገኛሉ፡፡
ማንቼስተር ዩናይትድ የነገውን ጨዋታ የሚያሸንፍ ከሆነ ቀሪ ጨዋታዎች እያሉት የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ተሳትፎውን የሚያረጋግጥ ይሆናል፡፡
ባለሜዳው ቡድን ማንቼስተር ዩናይትድ በሊጉ ሦስተኛ ተከታታይ ድሉን ለማሳካት ወደ ሜዳ የሚገባ ይሆናል፡፡
ሊቨርፑል በበኩሉ አራተኛ ተከታታይ ጨዋታውን ድል ለማድረግ የሚያደርገው ፍልሚያ ተጠባቂ ነው፡፡
ሁለቱ ቡድኖች እርስ በርስ ካደረጓቸው ያለፉት አምስት ጨዋታዎች ሊቨርፑል ሁለቱን ሲያሸንፍ ማንቼስተር ዩናይትድ በአንዱ ድል አድርጎ በቀሪ ሁለት ጨዋታዎች አቻ ተለያይተዋል፡፡
በዕለቱ ቀን 10 ሰዓት ላይ ቦርንማውዝ ከክሪስታል ፓላስ እንዲሁም ምሽት 3 ሰዓት ላይ አስቶንቪላ ከቶተንሃም ሆትስፐር ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡
የ35ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ሰኞ ምሽት በሚደረጉ ሁለት ጨዋታዎች ይጠናቀቃል፡፡
በዕለቱ ማንቼስተር ሲቲ ከሜዳው ውጪ ተጉዞ ምሽት 4 ሰዓት ላይ ከኤቨርተን ጋር የሚያደርገው ጨዋታ ተጠባቂ ነው፡፡
የአርሰናልን ውጤት አይቶ የሚጫወተው ማንቼስተር ሲቲ ለዋንጫው የሚያደርገውን ፉክክር አጠናክሮ ለመቀጠል ወደ ሜዳ የሚገባ ይሆናል፡፡
ከዚህ ጨዋታ አስቀድሞ ሰኞ ቀን 11 ሰዓት ቼልሲ ከሊጉ ላለመውረድ እየተፋለመ የሚገኘውን ኖቲንግሃም ፎረስት በስታምፎርድ ብሪጅ ያስተናግዳል፡፡
በወንድማገኝ ጸጋዬ
አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 24፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ35ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር አርሰናል በሜዳው ኢምሬትስ ምሽት 1 ሰዓት 30 ላይ ፉልሃምን ያስተናግዳል፡፡
ሊጉን ከተከታዩ ማንቼስተር ሲቲ በሦስት ነጥብ ልዩነት እየመራ የሚገኘው አርሰናል ከዚህ በኋላ የሚያደርጋቸው ጨዋታዎች ለዋንጫው በሚያደርገው ጉዞ ውስጥ ወሳኝ ናቸው፡፡
የካራባኦ ካፕ ዋንጫ ያጣውና ከኤፍ ኤ ውድድር የተሰናበተው አርሰናል በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ እና በአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ዋንጫውን ለማንሳት የሚያደርገው ጉዞ ይጠበቃል፡፡
በሊጉ ከተከታታይ ሁለት ጨዋታዎች ሽንፈት በኋላ ባሳለፍነው ሳምንት ኒውካስል ዩናይትድን በማሸነፍ ወደ ድል የተመለሰው አርሰናል ተከታታይ ጨዋታ በሊጉ ድል ለማድረግ ወደ ሜዳ የሚገባ ይሆናል፡፡
ተጋጣሚው ፉልሃም ከሁለት ተከታታይ ጨዋታዎች ድል አልባ ጉዞ በኋላ ባሳለፍነው ሳምንት ወደ ድል የተመለሰ ሲሆን አሸናፊነቱን ለማስቀጠል ብርቱ ፉክክር ያደርጋል ተብሎ ይጠበቃል፡፡
ሁለቱ ቡድኖች እርስ በርስ ካደረጓቸው ያለፉት አምስት ጨዋታዎች አርሰናል በሁለቱ ሲያሸንፍ፥ ፉልሃም በአንዱ ድል አድርጎ በቀሪ ሁለት ጨዋታዎች ደግሞ አቻ ተለያይተዋል፡፡
አርሰናል የዛሬ ምሽቱን ጨዋታ የሚያሸንፍ ከሆነ ማንቼስተር ሲቲ ሰኞ ምሽት ጨዋታውን እስከሚያደርግ ድረስ የነጥብ ልዩነቱን ወደ ስድስት ከፍ ማድረግ ይችላል፡፡
መውረዱን አስቀድሞ ያረጋገጠው ወልቭስ ከሰንደርላንድ፣ ኒውካስል ዩናይትድ ከብራይተን እንዲሁም ብሬንትፎርድ ከዌስትሃም ዩናይትድ በተመሳሳይ አመሻሽ 11 ሰዓት ላይ የሚደረጉ የዛሬ ጨዋታዎች ናቸው፡፡
ነገ የሊጉ ጨዋታ ሲቀጥል ማንቼስተር ዩናይትድ በሜዳው ኦልድትራፎርድ አመሻሽ 11 ሰዓት 30 ላይ ሊቨርፑልን ያስተናግዳል፡፡
ሁለቱም ቡድኖች የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ተሳትፎ ቦታን ለማግኘት እየተፋለሙ ይገኛሉ፡፡
ማንቼስተር ዩናይትድ የነገውን ጨዋታ የሚያሸንፍ ከሆነ ቀሪ ጨዋታዎች እያሉት የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ተሳትፎውን የሚያረጋግጥ ይሆናል፡፡
ባለሜዳው ቡድን ማንቼስተር ዩናይትድ በሊጉ ሦስተኛ ተከታታይ ድሉን ለማሳካት ወደ ሜዳ የሚገባ ይሆናል፡፡
ሊቨርፑል በበኩሉ አራተኛ ተከታታይ ጨዋታውን ድል ለማድረግ የሚያደርገው ፍልሚያ ተጠባቂ ነው፡፡
ሁለቱ ቡድኖች እርስ በርስ ካደረጓቸው ያለፉት አምስት ጨዋታዎች ሊቨርፑል ሁለቱን ሲያሸንፍ ማንቼስተር ዩናይትድ በአንዱ ድል አድርጎ በቀሪ ሁለት ጨዋታዎች አቻ ተለያይተዋል፡፡
በዕለቱ ቀን 10 ሰዓት ላይ ቦርንማውዝ ከክሪስታል ፓላስ እንዲሁም ምሽት 3 ሰዓት ላይ አስቶንቪላ ከቶተንሃም ሆትስፐር ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡
የ35ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ሰኞ ምሽት በሚደረጉ ሁለት ጨዋታዎች ይጠናቀቃል፡፡
በዕለቱ ማንቼስተር ሲቲ ከሜዳው ውጪ ተጉዞ ምሽት 4 ሰዓት ላይ ከኤቨርተን ጋር የሚያደርገው ጨዋታ ተጠባቂ ነው፡፡
የአርሰናልን ውጤት አይቶ የሚጫወተው ማንቼስተር ሲቲ ለዋንጫው የሚያደርገውን ፉክክር አጠናክሮ ለመቀጠል ወደ ሜዳ የሚገባ ይሆናል፡፡
ከዚህ ጨዋታ አስቀድሞ ሰኞ ቀን 11 ሰዓት ቼልሲ ከሊጉ ላለመውረድ እየተፋለመ የሚገኘውን ኖቲንግሃም ፎረስት በስታምፎርድ ብሪጅ ያስተናግዳል፡፡
በወንድማገኝ ጸጋዬ