5 days ago
(ዘ-ሐበሻ ስፖርት) የኒውካስሉ ተወዳጅ የቀድሞ አሰልጣኝ ኬቨን ኪጋን ካረፉ ገና አስር ቀናት ብቻ ቢቆጠሩም፣ ክለቡ ሌላ ያልተጠበቀ መርዶ አስተናግዷል፦ የኪጋንን ህልም እውን በማድረግ ክለቡን ለክብር ያበቁት አሰልጣኝ ኤዲ ሃው ከኃላፊነታቸው መልቀቃቸውን ይፋ አድርገዋል።
ከእጅግ አስከፊው የ2025-26 የውድድር ዘመን በኋላ በኃላፊነታቸው ለመቀጠል እና ክለቡን መልሰው ለመገንባት ቃል ገብተው የነበሩት ኤዲ ሃው፣ አዲሱ የፕሪሚየር ሊግ የውድድር ዘመን ሊጀመር ሶስት ሳምንታት ብቻ ሲቀሩት ውሳኔያቸውን ቀልብሰዋል።
ማክሰኞ ምሽት በቅድመ-ውድድር ዝግጅት ኒውካስል ከብሪስቶል ሲቲ ጋር ባደረገው የወዳጅነት ጨዋታ 4-1 በሆነ አሳፋሪ ውጤት መሸነፉ ብዙ ነገሮችን የቀየረ ይመስላል። ከሜዳቸው ውጪ ስታዲየሙን ሞልተው የነበሩት የኒውካስል ደጋፊዎች ያሰሙት የተቃውሞ እና የቁጣ ድምፅ፣ ይህ "ትርጉም አልባ" የሚመስል የወዳጅነት ጨዋታ ትልቅ መዘዝ ይዞ እንደሚመጣ አመላካች ነበር።
በማግስቱ ረቡዕ ጠዋት እንደተሰማው ኤዲ ሃው ኃላፊነታቸውን ለመልቀቅ ወስነዋል። የቅርብ ምንጮች እንደሚያሳዩት ይህ ውሳኔ የቅጽበት የብስጭት ውሳኔ ሳይሆን፣ ከከባዱ የውድድር ዘመን መገባደጃ አንስቶ አሰልጣኙ በውስጣቸው ሲያብሰለስሉት የቆዩት እና ሊሸከሙት ያልቻሉት ከባድ ሸክም ውጤት ነው።
ለኤዲ ሃው፣ ይህ ስንብት እጅግ አስደናቂ ለነበረው የኒውካስል ቆይታቸው የማይመጥን አሳዛኝ ማብቂያ ነው። ከ30 ዓመታት በፊት ኬቨን ኪጋን እጅግ ተቃርበውት የነበረውን፣ ደጋፊውም ለ70 ዓመታት ሲናፍቀው የነበረውን ትልቅ ዋንጫ ወደ ሴንት ጀምስ ፓርክ ያመጡት እርሳቸው ነበሩ።
እ.ኤ.አ በ2021 ክለቡ በፕሪሚየር ሊጉ 19ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጦ ወደ መውረድ አፋፍ በደረሰበት ወቅት ኃላፊነቱን የተረከቡት ሃው፣ ኒውካስልን በሊጉ ማቆየት ብቻ ሳይሆን በሚቀጥለው ዓመት ወደ ቻምፒዮንስ ሊግ መድረክ መልሰውታል። በ2024-25 ደግሞ በካራባኦ ካፕ የፍጻሜ ጨዋታ የሊጉን ሻምፒዮን ሊቨርፑልን በዌምብሌይ አሸንፈው ታሪካዊ ዋንጫ በማንሳት ስማቸውን በኒውካስል ታሪክ በወርቅ ቀለም አጽፈው ነበር።
ይህ የዋንጫ ድል የሳዑዲው የኢንቨስትመንት ፈንድ (PIF) በባለቤትነት ለሚያስተዳድረው እና የፕሪሚየር ሊጉን ዋንጫ ለሚያልመው ኒውካስል እንደ ትልቅ መነሻ መታየት ነበረበት። ሆኖም፣ የ2025ቱ ክረምት የሁሉንም ነገር አቅጣጫ ቀየረው።
በተለይም አሌክሳንደር ኢሳክን በክለቡ ለማቆየት የተደረገው ተስፋ አስቆራጭ እና መራር ትግል፣ በመጨረሻም ስዊድናዊው አጥቂ በብሪታንያ የዝውውር ሪከርድ በዝውውር መስኮቱ መዘጋጃ ዕለት ወደ ሊቨርፑል ማምራቱ ክለቡን ክፉኛ ጎድቶታል። ኒውካስል የኢሳክን ክፍተት ሊተካ የሚችል ተጫዋች ማምጣት አልቻለም። እንደ ሁጎ ኤኪቲኬ፣ ቤንጃሚን ሴስኮ እና ጆአዎ ፔድሮ ያሉ ታላላቅ ኢላማዎቹን ለተቀናቃኝ የፕሪሚየር ሊግ ክለቦች አሳልፎ ሰጠ።
በምትኩ ክለቡ እና ኤዲ ሃው በጋራ ያመጧቸው ኒክ ዎልቴማዴ፣ ዮአን ዊሳ እና አንቶኒ ኤላንጋ አጠቃላይ 180 ሚሊዮን ፓውንድ ($243m) ቢወጣባቸውም፣ ያሳዩት አቋም እና የገጠማቸው የጉዳት ችግር የተከፈለባቸውን ዋጋ ፈጽሞ ሊያጸድቅ አልቻለም። የኤላንጋ እና ዎልቴማዴ ብቃት ሲዋዥቅ፣ አጥቂው ዊሳ በሙሉ የውድድር ዘመኑ በሊጉ ያስቆጠረው አንድ ጎል ብቻ ነበር። በ43 ሚሊዮን ፓውንድ የመጣው ጃኮብ ራምሴይም በቁርጭምጭሚት ጉዳት ሲሰቃይ ጊዜውን አሳልፏል።
የዝውውር ውድቀቱ በሜዳ ላይ ውጤት ቢሸፈን ኖሮ የኤዲ ሃው ጫና ያን ያህል አይከፋም ነበር። ሆኖም የ2025-26 የውድድር ዘመን ለኒውካስል እውነተኛ ቅዠት ሆኖ አለፈ።
በዓመቱ መጀመሪያ ጥሩ አጀማመር ያሳየው ክለቡ፣ ከአዲሱ ዓመት በኋላ ግን የመውረድ ስጋት ወዳለባቸው ቡድኖች ወረደ። ከጥር መጨረሻ አንስቶ እስከ የውድድር ዘመኑ ማብቂያ ድረስ ካደረጋቸው 16 ጨዋታዎች በ10ሩ በመሸነፉ፣ ከ6ኛ ደረጃ ወደ 12ኛ ደረጃ በማሽቆልቆል ደጋፊውን በሀዘን እና በቁጣ ሞላው።
ይባስ ብሎ በኤፍኤ ካፕ እና በካራባኦ ካፕ በማንችስተር ሲቲ በቀላሉ ሲሰናበት፣ በቻምፒዮንስ ሊጉ ደግሞ ባርሴሎና በድምር ውጤት 8-3 በሆነ አሳፋሪ የጎል ናዳ አዋርዶ ከውድድሩ አስወጣው።
የኤዲ ሃው የወደፊት እጣ ፈንታ ጥያቄ ውስጥ የገባው ገና በጊዜ ነበር። በሚያዝያ ወር ኒውካስል በተከታታይ ለሶስተኛ ጊዜ በቦርንማውዝ ከተሸነፈ በኋላ፣ የክለቡ ታሪካዊ ሌጀንድ አላን ሺረር እንዲህ ብሎ ነበር፦ "ለኤዲ ምን ያህል ከባድ ጊዜ እንደሆነ ባውቅም፣ የወደፊት እጣ ፈንታው ምን እንደሚሆን አላውቅም። ዳግም የመዋጋት እና ክለቡን የማንሳት አቅሙ ያለው አይመስለኝም። በሚቀጥለው የውድድር ዘመን ኤዲ ሃው ኒውካስልን ያሰለጥናል ብዬ አላስብም።"
ሺረር እንዳለውም ሆነ ኤዲ ሃው ኒውካስልን ወደ ቀደመ ክብሩ የመመለስ ትልቅ ታሪክ ሰርተው፣ ነገር ግን በኋለኛው አመታቸው በዝውውር ውድቀት እና በሜዳ ላይ አስከፊ ውጤቶች ታጅበው የሴንት ጀምስ ፓርኩን በር ዘግተው ወጥተዋል።
ከእጅግ አስከፊው የ2025-26 የውድድር ዘመን በኋላ በኃላፊነታቸው ለመቀጠል እና ክለቡን መልሰው ለመገንባት ቃል ገብተው የነበሩት ኤዲ ሃው፣ አዲሱ የፕሪሚየር ሊግ የውድድር ዘመን ሊጀመር ሶስት ሳምንታት ብቻ ሲቀሩት ውሳኔያቸውን ቀልብሰዋል።
ማክሰኞ ምሽት በቅድመ-ውድድር ዝግጅት ኒውካስል ከብሪስቶል ሲቲ ጋር ባደረገው የወዳጅነት ጨዋታ 4-1 በሆነ አሳፋሪ ውጤት መሸነፉ ብዙ ነገሮችን የቀየረ ይመስላል። ከሜዳቸው ውጪ ስታዲየሙን ሞልተው የነበሩት የኒውካስል ደጋፊዎች ያሰሙት የተቃውሞ እና የቁጣ ድምፅ፣ ይህ "ትርጉም አልባ" የሚመስል የወዳጅነት ጨዋታ ትልቅ መዘዝ ይዞ እንደሚመጣ አመላካች ነበር።
በማግስቱ ረቡዕ ጠዋት እንደተሰማው ኤዲ ሃው ኃላፊነታቸውን ለመልቀቅ ወስነዋል። የቅርብ ምንጮች እንደሚያሳዩት ይህ ውሳኔ የቅጽበት የብስጭት ውሳኔ ሳይሆን፣ ከከባዱ የውድድር ዘመን መገባደጃ አንስቶ አሰልጣኙ በውስጣቸው ሲያብሰለስሉት የቆዩት እና ሊሸከሙት ያልቻሉት ከባድ ሸክም ውጤት ነው።
ለኤዲ ሃው፣ ይህ ስንብት እጅግ አስደናቂ ለነበረው የኒውካስል ቆይታቸው የማይመጥን አሳዛኝ ማብቂያ ነው። ከ30 ዓመታት በፊት ኬቨን ኪጋን እጅግ ተቃርበውት የነበረውን፣ ደጋፊውም ለ70 ዓመታት ሲናፍቀው የነበረውን ትልቅ ዋንጫ ወደ ሴንት ጀምስ ፓርክ ያመጡት እርሳቸው ነበሩ።
እ.ኤ.አ በ2021 ክለቡ በፕሪሚየር ሊጉ 19ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጦ ወደ መውረድ አፋፍ በደረሰበት ወቅት ኃላፊነቱን የተረከቡት ሃው፣ ኒውካስልን በሊጉ ማቆየት ብቻ ሳይሆን በሚቀጥለው ዓመት ወደ ቻምፒዮንስ ሊግ መድረክ መልሰውታል። በ2024-25 ደግሞ በካራባኦ ካፕ የፍጻሜ ጨዋታ የሊጉን ሻምፒዮን ሊቨርፑልን በዌምብሌይ አሸንፈው ታሪካዊ ዋንጫ በማንሳት ስማቸውን በኒውካስል ታሪክ በወርቅ ቀለም አጽፈው ነበር።
ይህ የዋንጫ ድል የሳዑዲው የኢንቨስትመንት ፈንድ (PIF) በባለቤትነት ለሚያስተዳድረው እና የፕሪሚየር ሊጉን ዋንጫ ለሚያልመው ኒውካስል እንደ ትልቅ መነሻ መታየት ነበረበት። ሆኖም፣ የ2025ቱ ክረምት የሁሉንም ነገር አቅጣጫ ቀየረው።
በተለይም አሌክሳንደር ኢሳክን በክለቡ ለማቆየት የተደረገው ተስፋ አስቆራጭ እና መራር ትግል፣ በመጨረሻም ስዊድናዊው አጥቂ በብሪታንያ የዝውውር ሪከርድ በዝውውር መስኮቱ መዘጋጃ ዕለት ወደ ሊቨርፑል ማምራቱ ክለቡን ክፉኛ ጎድቶታል። ኒውካስል የኢሳክን ክፍተት ሊተካ የሚችል ተጫዋች ማምጣት አልቻለም። እንደ ሁጎ ኤኪቲኬ፣ ቤንጃሚን ሴስኮ እና ጆአዎ ፔድሮ ያሉ ታላላቅ ኢላማዎቹን ለተቀናቃኝ የፕሪሚየር ሊግ ክለቦች አሳልፎ ሰጠ።
በምትኩ ክለቡ እና ኤዲ ሃው በጋራ ያመጧቸው ኒክ ዎልቴማዴ፣ ዮአን ዊሳ እና አንቶኒ ኤላንጋ አጠቃላይ 180 ሚሊዮን ፓውንድ ($243m) ቢወጣባቸውም፣ ያሳዩት አቋም እና የገጠማቸው የጉዳት ችግር የተከፈለባቸውን ዋጋ ፈጽሞ ሊያጸድቅ አልቻለም። የኤላንጋ እና ዎልቴማዴ ብቃት ሲዋዥቅ፣ አጥቂው ዊሳ በሙሉ የውድድር ዘመኑ በሊጉ ያስቆጠረው አንድ ጎል ብቻ ነበር። በ43 ሚሊዮን ፓውንድ የመጣው ጃኮብ ራምሴይም በቁርጭምጭሚት ጉዳት ሲሰቃይ ጊዜውን አሳልፏል።
የዝውውር ውድቀቱ በሜዳ ላይ ውጤት ቢሸፈን ኖሮ የኤዲ ሃው ጫና ያን ያህል አይከፋም ነበር። ሆኖም የ2025-26 የውድድር ዘመን ለኒውካስል እውነተኛ ቅዠት ሆኖ አለፈ።
በዓመቱ መጀመሪያ ጥሩ አጀማመር ያሳየው ክለቡ፣ ከአዲሱ ዓመት በኋላ ግን የመውረድ ስጋት ወዳለባቸው ቡድኖች ወረደ። ከጥር መጨረሻ አንስቶ እስከ የውድድር ዘመኑ ማብቂያ ድረስ ካደረጋቸው 16 ጨዋታዎች በ10ሩ በመሸነፉ፣ ከ6ኛ ደረጃ ወደ 12ኛ ደረጃ በማሽቆልቆል ደጋፊውን በሀዘን እና በቁጣ ሞላው።
ይባስ ብሎ በኤፍኤ ካፕ እና በካራባኦ ካፕ በማንችስተር ሲቲ በቀላሉ ሲሰናበት፣ በቻምፒዮንስ ሊጉ ደግሞ ባርሴሎና በድምር ውጤት 8-3 በሆነ አሳፋሪ የጎል ናዳ አዋርዶ ከውድድሩ አስወጣው።
የኤዲ ሃው የወደፊት እጣ ፈንታ ጥያቄ ውስጥ የገባው ገና በጊዜ ነበር። በሚያዝያ ወር ኒውካስል በተከታታይ ለሶስተኛ ጊዜ በቦርንማውዝ ከተሸነፈ በኋላ፣ የክለቡ ታሪካዊ ሌጀንድ አላን ሺረር እንዲህ ብሎ ነበር፦ "ለኤዲ ምን ያህል ከባድ ጊዜ እንደሆነ ባውቅም፣ የወደፊት እጣ ፈንታው ምን እንደሚሆን አላውቅም። ዳግም የመዋጋት እና ክለቡን የማንሳት አቅሙ ያለው አይመስለኝም። በሚቀጥለው የውድድር ዘመን ኤዲ ሃው ኒውካስልን ያሰለጥናል ብዬ አላስብም።"
ሺረር እንዳለውም ሆነ ኤዲ ሃው ኒውካስልን ወደ ቀደመ ክብሩ የመመለስ ትልቅ ታሪክ ሰርተው፣ ነገር ግን በኋለኛው አመታቸው በዝውውር ውድቀት እና በሜዳ ላይ አስከፊ ውጤቶች ታጅበው የሴንት ጀምስ ፓርኩን በር ዘግተው ወጥተዋል።
15 days ago
እንግሊዝ ባለታሪኳን በሞት ተነጠቀች
#ethiopia | የቀድሞ የኢንግሊዝ ብሔራዊ ቡድን አምበል እና አሰልጣኝ ኬቪን ኪጋን በ75 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ።
የኪጋን ቤተሰቦች ለረጅም ጊዜያት ሲታገልበት በቆየው የካንሰር ህመም ምክንያት ዛሬ ሰኞ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል ብለዋል።
ኬቪን ኪጋን በሊቨርፑል፣ በኒውካስል ዩናይትድ እና በጀርመኑ ሃምቡርግ በነበራቸው ቆይታ የማይረሱ ገድሎችን ፈጽሟል።
በ1978 እና 1979 ሁለት ጊዜ የባሎንዶር (Ballon d'Or) ሽልማትን በማሸነፍ በአውሮፓ እግር ኳስ ታሪክ ውስጥ ስሙ በወርቅ ቀለም ተጽፎለታል።
ኪጋን በአሰልጣኝነት ኒውካስል ዩናይትድን፣ የኢንግሊዝ ብሔራዊ ቡድንን፣ ማንቸስተር ሲቲን እና ፉልሀምን በመምራት በስፖርቱ ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ አሳድረዋል።
የእግር ኳስ ቤተሰቡ እና የተለያዩ ክለቦች በኬጋን ህልፈት ጥልቅ ሀዘናቸውን በመግለፅ ላይ ይገኛሉ።
ሔኖክ ወ/ገብርኤል
#ethiopia #getutemesgen #getunews #englandkevenkeegan #liverpoolnewcastel
#ethiopia | የቀድሞ የኢንግሊዝ ብሔራዊ ቡድን አምበል እና አሰልጣኝ ኬቪን ኪጋን በ75 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ።
የኪጋን ቤተሰቦች ለረጅም ጊዜያት ሲታገልበት በቆየው የካንሰር ህመም ምክንያት ዛሬ ሰኞ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል ብለዋል።
ኬቪን ኪጋን በሊቨርፑል፣ በኒውካስል ዩናይትድ እና በጀርመኑ ሃምቡርግ በነበራቸው ቆይታ የማይረሱ ገድሎችን ፈጽሟል።
በ1978 እና 1979 ሁለት ጊዜ የባሎንዶር (Ballon d'Or) ሽልማትን በማሸነፍ በአውሮፓ እግር ኳስ ታሪክ ውስጥ ስሙ በወርቅ ቀለም ተጽፎለታል።
ኪጋን በአሰልጣኝነት ኒውካስል ዩናይትድን፣ የኢንግሊዝ ብሔራዊ ቡድንን፣ ማንቸስተር ሲቲን እና ፉልሀምን በመምራት በስፖርቱ ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ አሳድረዋል።
የእግር ኳስ ቤተሰቡ እና የተለያዩ ክለቦች በኬጋን ህልፈት ጥልቅ ሀዘናቸውን በመግለፅ ላይ ይገኛሉ።
ሔኖክ ወ/ገብርኤል
#ethiopia #getutemesgen #getunews #englandkevenkeegan #liverpoolnewcastel
2 months ago
ሻምፒዮኑ አርሰናል ከሻምፒዮንሺፑ አሸናፊ ኮቬንትሪ ሲቲ …
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 13፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የ2026/27 የውድድር ዘመን የጨዋታ መርሐ ግብር በትናንትናው ዕለት ይፋ መደረጉ ይታወቃል፡፡
በዚህም የወቅቱ የሊጉ ሻምፒዮን አርሰናል ከሻምፒዮንሺፑ አሸናፊ ኮቬንትሪ ሲቲ ጋር በሜዳው ኢምሬትስ የሊጉን የመክፈቻ ጨዋታ ያደርጋል፡፡
ኮቬንትሪ ሲቲ ለመጨረሻ ጊዜ በአንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የተሳተፈው በ2000/01 የውድድር ዓመት እንደነበር ይታወሳል፡፡
በዚያ የውድድር ዓመት በሊጉ ካደረጋቸው 38 ጨዋታዎች 34 ነጥብ በመሰብሰብ 19ኛ ደረጃን ይዞ ወደ ሻምፒዮንሺፕ ለመውረድ ተገዷል፡፡
ክለቡ በአሰልጣኝ ፍራንክ ላምፓርድ እየተመራ ከዓመታት በኋላ በአስደናቂ ብቃት
ለ2026/27 የውድድር ዘመን ወደ ፕሪሚየር ሊጉ ማደጉ ይታወሳል፡፡
የ2026/27 የውድድር ዓመት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የመክፈቻ ጨዋታ የፕሪሚየር ሊጉና የሻምፒዮንሺፑ አሸናፊ ቡድኖች በሚያደርጉት ጨዋታ ይጀምራል፡፡
አርሰናል በ3ኛ ሳምንት የሊጉ መርሐ ግብር በሜዳው ቼልሲን የሚያስተናግድበት የለንደን ደርቢ ጨዋታ ተጠባቂ ነው፡፡
አርሰናል በ9ኛ ሳምንት ከሊቨርፑል፣ በ12ኛ ሳምንት ከማንቼስተር ሲቲ፣ በ14ኛ ሳምንት ከቶተንሃም ሆትስፐር እንዲሁም በ16ኛ ሳምንት ከማንቼስተር ዩናይትድ ጋር ይገናኛል፡፡
ከአሰልጣኝ ፔፕ ጋርዲዮላ ጋር በመለያየት አሰልጣኝ ኢንዞ ማሬስካን በኃላፊነት የሾመው ማንችስተር ሲቲ በሜዳው ከቦርንማውዝ ጋር የመጀመሪያ ሳምንት ጨዋታውን የሚያደርግ ይሆናል፡፡
አሰልጣኝ ኢንዞ ማሬስካ በማንቼስተር ሲቲ ቤት ከዚህ ቀደም በምክትል አሰልጣኝነት የሰሩ ሲሆን፥ በአዲሱ የውድድር ዓመት በዋና አሰልጣኝነት የሚያደርጉት ጉዞ ይጠበቃል፡፡
ማንቼስተር ሲቲ ከማንቼስተር ዩናይትድ ጋር በ4ኛ ሳምንት እንዲሁም ከሊቨርፑል ጋር በ6ኛ ሳምንት መርሐ ግብር ይገናኛል።
በአሰልጣኝ ማይክል ካሪክ የሚመራው ማንቼስተር ዩናይትድ በበኩሉ ከአዲስ አዳጊው ሃል ሲቲ ጋር በመጀመሪያ ሳምንት ጨዋታው ይገናኛል፡፡
ማንቼስተር ዩናይትድ ከአሰልጣኝ ማይክል ካሪክ ቅጥር በኋላ በመሻሻል የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ተሳትፎ ቦታን በማግኘት የውድድር ዓመቱን ማጠናቀቁ ይታወሳል፡፡
ከ4ኛ ሳምንት የማንቼስተር ደርቢ ጨዋታ በኋላ በ9ኛ ሳምንት ከቼልሲ፣ በ11ኛ ሳምንት ከሊቨርፑል እንዲሁም በ16ኛ ሳምንት ደግሞ ከወቅቱ የሊጉ ሻምፒዮን አርሰናል ጋር ይገናኛል፡፡
አንዶኒ ኢራዮላን በኋላፊነት የሾመው ሊቨርፑል ከኒውካስል ዩናይትድ የመጀመሪያ ሳምንት ጨዋታውን ያደርጋል፡፡
ሊቨርፑል በ6ኛ ሳምንት ከማንቼስተር ሲቲ፣ በ9ኛ ሳምንት ከአርሰናል፣ በ11ኛ ሳምንት ከማንቼስተር ዩናይትድ እንዲሁም በ12ኛ ሳምንት ደግሞ በመርሲሳይድ ደርቢ ከኤቨርተን ይፋለማል፡፡
ከአውሮፓ ውድድሮች ውጪ ሆኖ የውድድር ዓመቱን ያጠናቀቀው ቼልሲ በመጀመሪያ ሳምንት ከፉልሃም ጨዋታውን ያደርጋል፡፡
ቼልሲ አዲሱን የውድድር ዓመት በአሰልጣኝ ዣቢ አሎንሶ እየተመራ የሚጀምር ይሆናል፡፡
በመርሐ ግብሩ መሰረት አዲሱ የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የውድድር ዘመን ነሐሴ 15 ቀን 2018 ዓ.ም የሚጀመር ይሆናል፡፡
በወንድማገኝ ጸጋዬ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 13፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የ2026/27 የውድድር ዘመን የጨዋታ መርሐ ግብር በትናንትናው ዕለት ይፋ መደረጉ ይታወቃል፡፡
በዚህም የወቅቱ የሊጉ ሻምፒዮን አርሰናል ከሻምፒዮንሺፑ አሸናፊ ኮቬንትሪ ሲቲ ጋር በሜዳው ኢምሬትስ የሊጉን የመክፈቻ ጨዋታ ያደርጋል፡፡
ኮቬንትሪ ሲቲ ለመጨረሻ ጊዜ በአንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የተሳተፈው በ2000/01 የውድድር ዓመት እንደነበር ይታወሳል፡፡
በዚያ የውድድር ዓመት በሊጉ ካደረጋቸው 38 ጨዋታዎች 34 ነጥብ በመሰብሰብ 19ኛ ደረጃን ይዞ ወደ ሻምፒዮንሺፕ ለመውረድ ተገዷል፡፡
ክለቡ በአሰልጣኝ ፍራንክ ላምፓርድ እየተመራ ከዓመታት በኋላ በአስደናቂ ብቃት
ለ2026/27 የውድድር ዘመን ወደ ፕሪሚየር ሊጉ ማደጉ ይታወሳል፡፡
የ2026/27 የውድድር ዓመት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የመክፈቻ ጨዋታ የፕሪሚየር ሊጉና የሻምፒዮንሺፑ አሸናፊ ቡድኖች በሚያደርጉት ጨዋታ ይጀምራል፡፡
አርሰናል በ3ኛ ሳምንት የሊጉ መርሐ ግብር በሜዳው ቼልሲን የሚያስተናግድበት የለንደን ደርቢ ጨዋታ ተጠባቂ ነው፡፡
አርሰናል በ9ኛ ሳምንት ከሊቨርፑል፣ በ12ኛ ሳምንት ከማንቼስተር ሲቲ፣ በ14ኛ ሳምንት ከቶተንሃም ሆትስፐር እንዲሁም በ16ኛ ሳምንት ከማንቼስተር ዩናይትድ ጋር ይገናኛል፡፡
ከአሰልጣኝ ፔፕ ጋርዲዮላ ጋር በመለያየት አሰልጣኝ ኢንዞ ማሬስካን በኃላፊነት የሾመው ማንችስተር ሲቲ በሜዳው ከቦርንማውዝ ጋር የመጀመሪያ ሳምንት ጨዋታውን የሚያደርግ ይሆናል፡፡
አሰልጣኝ ኢንዞ ማሬስካ በማንቼስተር ሲቲ ቤት ከዚህ ቀደም በምክትል አሰልጣኝነት የሰሩ ሲሆን፥ በአዲሱ የውድድር ዓመት በዋና አሰልጣኝነት የሚያደርጉት ጉዞ ይጠበቃል፡፡
ማንቼስተር ሲቲ ከማንቼስተር ዩናይትድ ጋር በ4ኛ ሳምንት እንዲሁም ከሊቨርፑል ጋር በ6ኛ ሳምንት መርሐ ግብር ይገናኛል።
በአሰልጣኝ ማይክል ካሪክ የሚመራው ማንቼስተር ዩናይትድ በበኩሉ ከአዲስ አዳጊው ሃል ሲቲ ጋር በመጀመሪያ ሳምንት ጨዋታው ይገናኛል፡፡
ማንቼስተር ዩናይትድ ከአሰልጣኝ ማይክል ካሪክ ቅጥር በኋላ በመሻሻል የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ተሳትፎ ቦታን በማግኘት የውድድር ዓመቱን ማጠናቀቁ ይታወሳል፡፡
ከ4ኛ ሳምንት የማንቼስተር ደርቢ ጨዋታ በኋላ በ9ኛ ሳምንት ከቼልሲ፣ በ11ኛ ሳምንት ከሊቨርፑል እንዲሁም በ16ኛ ሳምንት ደግሞ ከወቅቱ የሊጉ ሻምፒዮን አርሰናል ጋር ይገናኛል፡፡
አንዶኒ ኢራዮላን በኋላፊነት የሾመው ሊቨርፑል ከኒውካስል ዩናይትድ የመጀመሪያ ሳምንት ጨዋታውን ያደርጋል፡፡
ሊቨርፑል በ6ኛ ሳምንት ከማንቼስተር ሲቲ፣ በ9ኛ ሳምንት ከአርሰናል፣ በ11ኛ ሳምንት ከማንቼስተር ዩናይትድ እንዲሁም በ12ኛ ሳምንት ደግሞ በመርሲሳይድ ደርቢ ከኤቨርተን ይፋለማል፡፡
ከአውሮፓ ውድድሮች ውጪ ሆኖ የውድድር ዓመቱን ያጠናቀቀው ቼልሲ በመጀመሪያ ሳምንት ከፉልሃም ጨዋታውን ያደርጋል፡፡
ቼልሲ አዲሱን የውድድር ዓመት በአሰልጣኝ ዣቢ አሎንሶ እየተመራ የሚጀምር ይሆናል፡፡
በመርሐ ግብሩ መሰረት አዲሱ የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የውድድር ዘመን ነሐሴ 15 ቀን 2018 ዓ.ም የሚጀመር ይሆናል፡፡
በወንድማገኝ ጸጋዬ
2 months ago
ሊቨርፑል እና ፒኤስጂ ለማስፈረም የሚፎካከሩበት ተጫዋች አይቮሪኮስታዊው ኮከብ ያን ዲዮማንዴ
https://youtu.be/7VN4DsSwl... #ebcdotstream #ebcsport
Sponsored by
Surafel
2 months ago
ዲቮክ ኦሪጊ ጫማውን ሰቅሏል !
#ethiopia | የቀድሞ የሊቨርፑል የፊት መስመር ተጨዋች ዲቮኮ ኦሪጊ ጫማውን መስቀሉን በይፋ አስታውቋል።
“ በትልቅ ደረጃ ተጫውቼ ትልቅ ዋንጫ በማሸነፍ ህልሜን ኖርያለሁ አሁን ተልዕኮዬ አብቅቷል “ ሲል ኦሪጊ በማህበራዊ ትስስር ገፁ ፅፏል።
የ 31ዓመቱ ኦሪጊ በሊቨርፑል የፕሪሚየር ሊግ እና ሻምፒየንስ ሊግ ዋንጫዎችን ማሸነፍ ችሏል።
በተጨማሪም ኤፌ ካፕ ፤ ሊግ ካፕ ፤ የክለቦች አለም ዋንጫ እና ዩኤፋ ሱፐር ካፕ አሳክቷል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #sport #addisababa #uk #ethiopia #tikvahethsport
#ethiopia | የቀድሞ የሊቨርፑል የፊት መስመር ተጨዋች ዲቮኮ ኦሪጊ ጫማውን መስቀሉን በይፋ አስታውቋል።
“ በትልቅ ደረጃ ተጫውቼ ትልቅ ዋንጫ በማሸነፍ ህልሜን ኖርያለሁ አሁን ተልዕኮዬ አብቅቷል “ ሲል ኦሪጊ በማህበራዊ ትስስር ገፁ ፅፏል።
የ 31ዓመቱ ኦሪጊ በሊቨርፑል የፕሪሚየር ሊግ እና ሻምፒየንስ ሊግ ዋንጫዎችን ማሸነፍ ችሏል።
በተጨማሪም ኤፌ ካፕ ፤ ሊግ ካፕ ፤ የክለቦች አለም ዋንጫ እና ዩኤፋ ሱፐር ካፕ አሳክቷል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #sport #addisababa #uk #ethiopia #tikvahethsport
2 months ago
ሊቨርፑል አንዶኒ ኢራዮላን ዋና አሰልጣኝ አድርጎ ሾመ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 27፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ሊቨርፑል አንዶኒ ኢራዮላን ዋና አሰልጣኝ አድርጎ መሾሙን ይፋ አድርጓል።
ላለፉት ሦስት ዓመታት ቦርንማውዝን የመሩት ስፔናዊው አሰልጣኝ በይፋ የመርሲሳይዱን ክለብ ኃላፊነት ተረክበዋል።
የ43 ዓመቱ አንዶኒ ኢራዮላ ቦርንማውዝን በታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ ለአውሮፓ መድረክ ያበቁ ሲሆን፥ ሊቨርፑልን በመረከባቸው መደሰታቸውን ገልጸዋል።
ሊቨርፑል ባሳለፍነው ቅዳሜ ዕለት አሰልጣኝ አርነ ስሎትን ማሰናበቱ ይታወሳል።
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 27፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ሊቨርፑል አንዶኒ ኢራዮላን ዋና አሰልጣኝ አድርጎ መሾሙን ይፋ አድርጓል።
ላለፉት ሦስት ዓመታት ቦርንማውዝን የመሩት ስፔናዊው አሰልጣኝ በይፋ የመርሲሳይዱን ክለብ ኃላፊነት ተረክበዋል።
የ43 ዓመቱ አንዶኒ ኢራዮላ ቦርንማውዝን በታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ ለአውሮፓ መድረክ ያበቁ ሲሆን፥ ሊቨርፑልን በመረከባቸው መደሰታቸውን ገልጸዋል።
ሊቨርፑል ባሳለፍነው ቅዳሜ ዕለት አሰልጣኝ አርነ ስሎትን ማሰናበቱ ይታወሳል።
2 months ago
አንዶኒ ኢራኦላ የሊቨርፑል አሰልጣኝ ሆኖ ተሾመ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 26፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ስፔናዊው አሰልጣኝ አንዶኒ ኢራኦላ አርነ ስሎትን በመተካት የሊቨርፑል አሰልጣኝ በመሆን ተሾሟል፡፡
በቦርንማውዝ አስደናቂ ቡድን መገንባት የቻለው ኢራኦላ በአንፊልዱ ክለብ እስከ ፈረንጆቹ 2028 የሚያቆየውን ኮንትራት መፈረሙ ተገልጿል፡፡
አሰልጣኙ በቆይታው ቡድኑን ወደ አሸናፊነት የመመለስ ሃላፊነት ተጥሎበታል፡፡
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 26፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ስፔናዊው አሰልጣኝ አንዶኒ ኢራኦላ አርነ ስሎትን በመተካት የሊቨርፑል አሰልጣኝ በመሆን ተሾሟል፡፡
በቦርንማውዝ አስደናቂ ቡድን መገንባት የቻለው ኢራኦላ በአንፊልዱ ክለብ እስከ ፈረንጆቹ 2028 የሚያቆየውን ኮንትራት መፈረሙ ተገልጿል፡፡
አሰልጣኙ በቆይታው ቡድኑን ወደ አሸናፊነት የመመለስ ሃላፊነት ተጥሎበታል፡፡
2 months ago
(ዘ-ሐበሻ ስፖርት) ፈረንሳያዊው ተከላካይ ኢብራሂማ ኮናቴ ወደ ስፔኑ ታላቅ ክለብ ሪያል ማድሪድ የሚያደርገው ዝውውር መገባደጃው ላይ መድረሱን ምንጮች አረጋገጡ። ባለፉት 48 ሰዓታት ውስጥ በተደረጉት የድርድር ሒደቶች ከፍተኛ መሻሻል የታየ ሲሆን፣ በቅርቡ 27ኛ ዓመት የልደት በዓሉን ያከበረው ኮናቴ በአራት ዓመት ኮንትራት እና በፊርማ ክፍያ ጉዳዮች ላይ ከስምምነት ለመድረስ ጥቂት ዝርዝር ጉዳዮች ብቻ ቀርተውታል።
የማድሪድ ኃላፊዎች በፓሪስ የተወለደውን ይህንን ተከላካይ ለማስፈረም ከወራት በፊት ጀምሮ ፍላጎት ያሳዩ ቢሆንም፣ የተጫዋቹ ቀዳሚ ምርጫ ግን በሊቨርፑል መቆየት ነበር። ይሁን እንጂ ከክለቡ ጋር አዲስ ኮንትራት ለመፈራረም ባለመቻሉ፣ እ.ኤ.አ. በ2021 ከሌይፕዚግ ተነስቶ ያቀናበትን አንፊልድን በነጻ ዝውውር ለመልቀቅ ተገዷል።
ኮናቴ ሊቨርፑልን እንደሚለቅ በተረጋገጠበት ወቅት ሪያል ማድሪድ ፈጣን ጥያቄ በማቅረብ ቀዳሚው ቢሆንም፣ ባየር ሙኒክን፣ ባርሴሎናን እና የሳውዲ ክለቦችን ጨምሮ ሌሎች በርካታ ክለቦች የተከላካዩን ፊርማ ለማግኘት ጥረት አድርገው እንደነበር ምንጮች ጠቁመዋል።
ይህ ዝውውር ዕውን የሚሆን ከሆነ፣ ኮናቴ በሳንቲያጎ በርናባው ከሚገኙት የፈረንሳይ ብሔራዊ ቡድን አጋሮቹ ኪሊያን ምባፔ፣ ኦሬልየን ቹአሜኒ፣ ኤድዋርዶ ካማቪንጋ እና ፈርላንድ ሜንዲ ጋር ዳግም ይገናኛል። ተጫዋቹ በዓለማችን ትልቁን ክለብ ለመቀላቀል መቃረቡ እጅግ እንዳስደሰተው የተገለጸ ሲሆን፣ በቀጣዩ ሳምንት ከፈረንሳይ ብሔራዊ ቡድን ጋር ወደ ዓለም ዋንጫው ከማምራቱ በፊት የዝውውር ሒደቱ ሙሉ በሙሉ ተጠናቆ ማየት ይፈልጋል።
የማድሪድ ኃላፊዎች በፓሪስ የተወለደውን ይህንን ተከላካይ ለማስፈረም ከወራት በፊት ጀምሮ ፍላጎት ያሳዩ ቢሆንም፣ የተጫዋቹ ቀዳሚ ምርጫ ግን በሊቨርፑል መቆየት ነበር። ይሁን እንጂ ከክለቡ ጋር አዲስ ኮንትራት ለመፈራረም ባለመቻሉ፣ እ.ኤ.አ. በ2021 ከሌይፕዚግ ተነስቶ ያቀናበትን አንፊልድን በነጻ ዝውውር ለመልቀቅ ተገዷል።
ኮናቴ ሊቨርፑልን እንደሚለቅ በተረጋገጠበት ወቅት ሪያል ማድሪድ ፈጣን ጥያቄ በማቅረብ ቀዳሚው ቢሆንም፣ ባየር ሙኒክን፣ ባርሴሎናን እና የሳውዲ ክለቦችን ጨምሮ ሌሎች በርካታ ክለቦች የተከላካዩን ፊርማ ለማግኘት ጥረት አድርገው እንደነበር ምንጮች ጠቁመዋል።
ይህ ዝውውር ዕውን የሚሆን ከሆነ፣ ኮናቴ በሳንቲያጎ በርናባው ከሚገኙት የፈረንሳይ ብሔራዊ ቡድን አጋሮቹ ኪሊያን ምባፔ፣ ኦሬልየን ቹአሜኒ፣ ኤድዋርዶ ካማቪንጋ እና ፈርላንድ ሜንዲ ጋር ዳግም ይገናኛል። ተጫዋቹ በዓለማችን ትልቁን ክለብ ለመቀላቀል መቃረቡ እጅግ እንዳስደሰተው የተገለጸ ሲሆን፣ በቀጣዩ ሳምንት ከፈረንሳይ ብሔራዊ ቡድን ጋር ወደ ዓለም ዋንጫው ከማምራቱ በፊት የዝውውር ሒደቱ ሙሉ በሙሉ ተጠናቆ ማየት ይፈልጋል።
2 months ago
ሻምፒዮኑ አርሰናል ሲያሸንፍ፣ ዌስትሀም ወረደ ቶተንሀም ተረፈ
ከሁለት አስርት ዓመታት በላይ የዘለቀው የመድፈኞቹ የዋንጫ ጥማት ዛሬ በደመቀ ሁኔታ ተቋጭቷል።
አርሰናል በ38ኛው ሳምንት የመጨረሻ ጨዋታው ክሪስታል ፓላስን 2 ለ 1 በሆነ ውጤት በማሸነፍ የሊጉን የክብር አክሊል ይረከባል።
በመጀመሪያው የጨዋታ ክፍለ ጊዜ ገብርኤል ጀሱስ ያስቆጠራት ግብ የድሉን መንገድ የጠረገች ሲሆን፤ ቡድኑ እስከ ጨዋታው ፍጻሜ ድረስ ብቃቱን በማስመስከር የለንደን ጎዳናዎችን በደስታ እና በእልልታ እንዲሞሉ አድርጓል።
በሌሎች የዛሬው የመጨረሻ ሳምንት መርሃ ግብሮች ማንቸስተር ሲቲ በአስቶን ቪላ 2 ለ 1 በሆነ ውጤት ሲሸነፍ፣ ማንቸስተር ዩናይትድ ብራይተንን 3 ለ 0 በሆነ ሰፊ ውጤት ረቷል።
ዌስትሃም ሊድስን በ 3 ለ 0 በሆነ ውጤት ቢያሸንፍም ወደታችኛው ሊግ ወርዷል።
ቶተንሃም ኤቨርተንን 1 ለ 0 አሸንፎ በሊጉ መቆየት ችሏል።
በሌላ በኩል ሊቨርፑል ከብሬንትፎርድ ጋር 1 ለ 1፣ ፉልሃም ኒውካስትልን 2 ለ 0፣ ሰንደርላንድ ቼልሲን 2 ለ 1 በማሸነፍ ያልተጠበቀ ውጤት አስመዝግቧል።
በርንሌይ ከዎልቭስ እንዲሁም ኖቲንግሃም ፎረስት ከቦርንማውዝ ጋር 1 ለ 1 በሆነ አቻ ውጤት የውድድር ዘመኑን አጠናቀዋል።
Seledadotio
Seledadotio
ከሁለት አስርት ዓመታት በላይ የዘለቀው የመድፈኞቹ የዋንጫ ጥማት ዛሬ በደመቀ ሁኔታ ተቋጭቷል።
አርሰናል በ38ኛው ሳምንት የመጨረሻ ጨዋታው ክሪስታል ፓላስን 2 ለ 1 በሆነ ውጤት በማሸነፍ የሊጉን የክብር አክሊል ይረከባል።
በመጀመሪያው የጨዋታ ክፍለ ጊዜ ገብርኤል ጀሱስ ያስቆጠራት ግብ የድሉን መንገድ የጠረገች ሲሆን፤ ቡድኑ እስከ ጨዋታው ፍጻሜ ድረስ ብቃቱን በማስመስከር የለንደን ጎዳናዎችን በደስታ እና በእልልታ እንዲሞሉ አድርጓል።
በሌሎች የዛሬው የመጨረሻ ሳምንት መርሃ ግብሮች ማንቸስተር ሲቲ በአስቶን ቪላ 2 ለ 1 በሆነ ውጤት ሲሸነፍ፣ ማንቸስተር ዩናይትድ ብራይተንን 3 ለ 0 በሆነ ሰፊ ውጤት ረቷል።
ዌስትሃም ሊድስን በ 3 ለ 0 በሆነ ውጤት ቢያሸንፍም ወደታችኛው ሊግ ወርዷል።
ቶተንሃም ኤቨርተንን 1 ለ 0 አሸንፎ በሊጉ መቆየት ችሏል።
በሌላ በኩል ሊቨርፑል ከብሬንትፎርድ ጋር 1 ለ 1፣ ፉልሃም ኒውካስትልን 2 ለ 0፣ ሰንደርላንድ ቼልሲን 2 ለ 1 በማሸነፍ ያልተጠበቀ ውጤት አስመዝግቧል።
በርንሌይ ከዎልቭስ እንዲሁም ኖቲንግሃም ፎረስት ከቦርንማውዝ ጋር 1 ለ 1 በሆነ አቻ ውጤት የውድድር ዘመኑን አጠናቀዋል።
Seledadotio
Seledadotio
2 months ago
መድፉ ተተኮሰ
#ethiopia | የእንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ ፍጻሜ አርሰናል በድል ሲያጠናቅቅ ቶተንሃም በሊጉ መትረፉን አረጋግጧል ማንችስተር ሲቲ ደግሞ ሽንፈት አስተናግዷል
የ2025/26 የእንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ የውድድር ዘመን ዛሬ በአንድ ሰዓት በተደረጉ አስር ጨዋታዎች ፍጻሜውን አግኝቷል።
ከ22 ዓመታት ረጅም ጥበቃ በኋላ የሊጉን ዘውድ የደፋው አርሰናል ወደ ክሪስታል ፓላስ ሜዳ በመጓዝ 2 ለ 1 በሆነ ውጤት ማሸነፍ ችሏል።
ለመድፈኞቹ የማሸነፊያ ግቦቹን ያስቆጠሩት ጋብርኤል ጄሱስ እና ኖኒ ማዱኤኬ ሲሆኑ ክለቡ የዓመቱን ጉዞ በ85 ነጥብ በበላይነት አጠናቋል።
ወደ ታችኛው ክፍል የመውረድ ከፍተኛ ስጋት ውስጥ የነበረው ቶተንሃም ሆትስፐርስ ኤቨርተንን 1 ለ 0 በማሸነፍ በሊጉ መቆየቱን አረጋግጧል።
ለለንደኑ ክለብ ወሳኟን የህልውና ግብ ያስቆጠረው ጆአኦ ፓልሂንሃ ነው። በሌላ በኩል ላለመውረድ ሲፋለም የነበረው ዌስትሃም ዩናይትድ ሊድስ ዩናይትድን 3 ለ 0 ቢያሸንፍም ከውድድር መውረዱን ሊያስቀር አልቻለም።
ክለቡ ከቶተንሃም በሁለት ነጥብ በማነሱ ምክንያት በርንሌይ እና ዎልቭስን ተከትሎ ወደ ቻምፒየንሺፕ ወርዷል።
ከማንችስተር ሲቲ ጋር ለመለያየት የወሰነው አሰልጣኝ ፔፕ ጋርዲዮላ በመጨረሻው የሊግ ጨዋታው በአስቶንቪላ 2 ለ 1 በሆነ ውጤት ሽንፈት ገጥሞታል።
ታዋቂ ተጫዋቾቹን ሞሐመድ ሳላህ እና አንዲ ሮበርትሰንን በክብር ያሰናበተው ሊቨርፑል ከብሬንትፎርድ ጋር ያደረገውን ጨዋታ በአቻ ውጤት አጠናቋል።
ለአሰልጣኝ ማይክል ካሪክ የአንድ ዓመት ተጨማሪ ውል ያበረከተው ማንችስተር ዩናይትድ ብራይተንን ከሜዳው ውጪ 3 ለ 0 በሆነ ሰፊ ውጤት አሸንፏል።
በዚህ ጨዋታ ላይ አንድ ግብ አስቆጥሮ ለሌላው ደግሞ አመቻችቶ ያቀበለው ብሩኖ ፈርናንዴዝ አዲስ ታሪክ አስመዝግቧል። ፖርቹጋላዊው አማካይ በአንድ የውድድር ዓመት ውስጥ 21 ግብ የሆኑ ኳሶችን በማመቻቸት ቀዳሚው ተጫዋች መሆን ችሏል።
ወደ ሊጉ በቅርቡ ያደገው ሰንደርላንድ ቼልሲን 2 ለ 1 በማሸነፍ በቀጣዩ ዓመት በአውሮፓ መድረክ ላይ የመሳተፍ መብቱን አግኝቷል።
በተያያዙ ዜናዎች ፉልሃም ኒውካስትል ዩናይትድን 2 ለ 0 ሲያሸንፍ ኖቲንግሃም ፎረስት ከቦርንማውዝ ጋር 1 ለ 1 ተለያይቷል።
ቀድመው መውረዳቸውን ያረጋገጡት በርንሌይ እና ዎልቭስ ያደረጉት ጨዋታም በተመሳሳይ 1 ለ 1 በሆነ አቻ ውጤት ተጠናቋል።
#የእንግሊዝፕሪምየርሊግ #አርሰናል #ቶተንሃም #ማንችስተርሲቲ #ማንችስተርዩናይትድ #ሊቨርፑል #እግርኳስ #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | የእንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ ፍጻሜ አርሰናል በድል ሲያጠናቅቅ ቶተንሃም በሊጉ መትረፉን አረጋግጧል ማንችስተር ሲቲ ደግሞ ሽንፈት አስተናግዷል
የ2025/26 የእንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ የውድድር ዘመን ዛሬ በአንድ ሰዓት በተደረጉ አስር ጨዋታዎች ፍጻሜውን አግኝቷል።
ከ22 ዓመታት ረጅም ጥበቃ በኋላ የሊጉን ዘውድ የደፋው አርሰናል ወደ ክሪስታል ፓላስ ሜዳ በመጓዝ 2 ለ 1 በሆነ ውጤት ማሸነፍ ችሏል።
ለመድፈኞቹ የማሸነፊያ ግቦቹን ያስቆጠሩት ጋብርኤል ጄሱስ እና ኖኒ ማዱኤኬ ሲሆኑ ክለቡ የዓመቱን ጉዞ በ85 ነጥብ በበላይነት አጠናቋል።
ወደ ታችኛው ክፍል የመውረድ ከፍተኛ ስጋት ውስጥ የነበረው ቶተንሃም ሆትስፐርስ ኤቨርተንን 1 ለ 0 በማሸነፍ በሊጉ መቆየቱን አረጋግጧል።
ለለንደኑ ክለብ ወሳኟን የህልውና ግብ ያስቆጠረው ጆአኦ ፓልሂንሃ ነው። በሌላ በኩል ላለመውረድ ሲፋለም የነበረው ዌስትሃም ዩናይትድ ሊድስ ዩናይትድን 3 ለ 0 ቢያሸንፍም ከውድድር መውረዱን ሊያስቀር አልቻለም።
ክለቡ ከቶተንሃም በሁለት ነጥብ በማነሱ ምክንያት በርንሌይ እና ዎልቭስን ተከትሎ ወደ ቻምፒየንሺፕ ወርዷል።
ከማንችስተር ሲቲ ጋር ለመለያየት የወሰነው አሰልጣኝ ፔፕ ጋርዲዮላ በመጨረሻው የሊግ ጨዋታው በአስቶንቪላ 2 ለ 1 በሆነ ውጤት ሽንፈት ገጥሞታል።
ታዋቂ ተጫዋቾቹን ሞሐመድ ሳላህ እና አንዲ ሮበርትሰንን በክብር ያሰናበተው ሊቨርፑል ከብሬንትፎርድ ጋር ያደረገውን ጨዋታ በአቻ ውጤት አጠናቋል።
ለአሰልጣኝ ማይክል ካሪክ የአንድ ዓመት ተጨማሪ ውል ያበረከተው ማንችስተር ዩናይትድ ብራይተንን ከሜዳው ውጪ 3 ለ 0 በሆነ ሰፊ ውጤት አሸንፏል።
በዚህ ጨዋታ ላይ አንድ ግብ አስቆጥሮ ለሌላው ደግሞ አመቻችቶ ያቀበለው ብሩኖ ፈርናንዴዝ አዲስ ታሪክ አስመዝግቧል። ፖርቹጋላዊው አማካይ በአንድ የውድድር ዓመት ውስጥ 21 ግብ የሆኑ ኳሶችን በማመቻቸት ቀዳሚው ተጫዋች መሆን ችሏል።
ወደ ሊጉ በቅርቡ ያደገው ሰንደርላንድ ቼልሲን 2 ለ 1 በማሸነፍ በቀጣዩ ዓመት በአውሮፓ መድረክ ላይ የመሳተፍ መብቱን አግኝቷል።
በተያያዙ ዜናዎች ፉልሃም ኒውካስትል ዩናይትድን 2 ለ 0 ሲያሸንፍ ኖቲንግሃም ፎረስት ከቦርንማውዝ ጋር 1 ለ 1 ተለያይቷል።
ቀድመው መውረዳቸውን ያረጋገጡት በርንሌይ እና ዎልቭስ ያደረጉት ጨዋታም በተመሳሳይ 1 ለ 1 በሆነ አቻ ውጤት ተጠናቋል።
#የእንግሊዝፕሪምየርሊግ #አርሰናል #ቶተንሃም #ማንችስተርሲቲ #ማንችስተርዩናይትድ #ሊቨርፑል #እግርኳስ #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
2 months ago
(ዘ-ሐበሻ ስፖርት) በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ታሪክ ከባህር ማዶ መጥቶ እንደ ግብጹ "የአባይ ውሃ ዘመዳችን" መሀመድ ሳላህ የጎል መረብን ያንቀጠቀጠ የለም፤ 193 የማይታመኑ ጎሎች! ታሪኩ የሚጀምረው ነሐሴ 12 ቀን 2017 ነው። ሊቨርፑል ዋትፎርድን ሲገጥም፣ አሰልጣኝ የርገን ክሎፕ አዲስ ፈራሚውን «ወደ ፕሪሚየር ሊጉ እንኳን በደህና መጣህ!» በሚል አጭርና ግልጽ መልዕክት ወደ ሜዳ ሰደዱት። ያኔ የተጠነሰሰው አስፈሪው የሳላህ፣ ማኔ እና ፊርሚኖ የአጥቂ መስመር ጥምረት አሰልጣኝ ፔፕ ጋርዲዮላን ጭምር «ያናውጡኛል፣ አደገኞች ናቸው» እስኪል ድረስ ዓለምን ጉድ አሰኝቷል።
ሳላህ እና ማኔ የቅርብ ጓደኛሞች ባይሆኑም፣ በመካከላቸው የነበረው ጤናማ ውድድር እና ፊርሚኖ በሁለቱ መሀል የሚነሳውን እሳት በማጥፋት የተጫወተው ሚና፣ የሊቨርፑልን የድል ጉዞ የጀርባ አጥንት ሆኗል። የቡድኑ አጋሮቹ «ለእግር ኳስ የተፈጠረ» ብለው የሚመሰክሩለት ሳላህ፣ በምሳሌነት የሚመራ [ይላል] እና ለዝርዝር ነገሮች ከፍተኛ ትኩረት የሚሰጥ ጽኑ ተዋጊ ነው። ዋትፎርድን 5 ለ 0 ባሸነፉበት ጨዋታ ላይ፣ ጨዋታው እንደተጠናቀቀ ግብ ጠባቂውን ቤን ፎስተርን «ፍጹም ቅጣት ምት ቢሆን ኖሮ ወደየትኛው አቅጣጫ ትዘል ነበር?» ብሎ መጠየቁ ለስራው ያለውን ቁርጠኝነት ያሳያል።
በአንፊልድ ቆይታው አንዳንዴ ተስፋ መቁረጥ እና ቁጣ ታይቶበት ያውቃል። ባለፈው ታህሳስ ከዋና አሰልጣኙ አርኔ ስሎት ጋር የነበረው አለመግባባት አሁን ላለው ስንብት መነሻ ሆኗል። ይህ የውድድር ዘመን ለሊቨርፑል ስብስብ እጅግ ከባድ የነበረ ሲሆን፣ የቡድን አጋሩ ዲዮጎ ጆታ ህይወት ማለፍ ሳላህን ክፉኛ ጎድቶታል። «ከእረፍት በኋላ ወደ ሊቨርፑል መመለስ እንደዚህ ያስፈራኛል ብዬ አስቤ አውቅም» ሲል ሀዘኑን ገልጾ፣ በአንፊልድ ፊት እምባውን በማፍሰስ ሰብዓዊነቱን አሳይቷል።
በሜዳ ላይ ግን ሳላህ ከተፈጥሮ በላይ ነበር። በአንፊልድ የመጀመሪያ የውድድር ዘመኑ 58 የጎል ተሳትፎዎችን (በየ 71 ደቂቃው አንድ ጎል ላይ ተሳትፎ) በማድረግ ሜሲ እና ሮናልዶ ካሉበት ደረጃ ደርሷል። ማድሪድ ላይ ቶተንሃምን አሸንፈው የሻምፒዮንስ ሊግ ዋንጫ ሲያነሱ፣ በጉዲሰን ፓርክ ኤቨርተን ላይ የፑስካስ አዋርድ ያሸነፈባትን ጎል ሲያገባ፣ እና በኦልድ ትራፎርድ ማንችስተር ዩናይትድ ላይ ያሳየው ጀብዱ... ትዝታዎቹ ማለቂያ የላቸውም። የሲቲው አይሜሪክ ላፖርት ጭምር «ሳላህ በእኛ ላይ ሁልጊዜ እሳት ይተፋ ነበር፤ ለመከላከል ከገጠሙኝ ከባድ ተጫዋቾች አንዱ ነው» በማለት ይመሰክራል።
ሸሚዙን አውልቆ ደስታውን ሲገልጽም ሆነ በሱጁድ ፈጣሪውን ሲያመሰግን፣ የሳላህ ምስሎች መቼም አይረሱም። የቀድሞው አምበል ስቲቨን ጀራርድ «ቁጥሮቹ፣ ዋንጫዎቹ እና የገነባው ባህል የራሳቸው ታሪክ ይናገራሉ። መሀመድ ሳላህ በሁላችንም ዘንድ የተወደደ የክለቡ እውነተኛ ጀግና ነው» ሲል አወድሶታል። ትሬንት አሌክሳንደር አርኖልድም ለክለቡ ያላቸውን ዋጋ ሲገልጽ ሳላህን እና ጀራርድን በእኩልነት አንደኛ ደረጃ ላይ አስቀምጧቸዋል።
የ2024-25 የውድድር ዘመን ሊቨርፑል 20ኛውን የሊግ ዋንጫ ሲያነሳ፣ ሳላህ ከፍተኛ ጎል እና አሲስት በማድረግ በእንግሊዝ እግር ኳስ ታሪክ ውስጥ ደማቅ አሻራ አሳርፏል። አሁን ግን ሁሉም ነገር ፍጻሜ አለው። ከግብጽ የናይል ዴልታ የተነሳው የዚህ ድንቅ ተዋጊ ጉዞ፣ በሜርሲሳይድ አንፊልድ ላይ የማይረሳ ታሪክ ጽፎ ወደሚቀጥለው ምዕራፍ ተሸጋግሯል። የርገን ክሎፕ እንዳሉት፣ «ሲመጣ ሰዎች ምን እንደሚያስቡ ሳይሆን፣ ሲሄድ ምን እንደሚያስቡ ማወቁ ነው ትልቁ ነገር»። መሀመድ ሳላህ... ለአንፊልድ ትክክለኛው ተዋጊ፣ በትክክለኛው ጊዜ የመጣው ጀግና!
ሳላህ እና ማኔ የቅርብ ጓደኛሞች ባይሆኑም፣ በመካከላቸው የነበረው ጤናማ ውድድር እና ፊርሚኖ በሁለቱ መሀል የሚነሳውን እሳት በማጥፋት የተጫወተው ሚና፣ የሊቨርፑልን የድል ጉዞ የጀርባ አጥንት ሆኗል። የቡድኑ አጋሮቹ «ለእግር ኳስ የተፈጠረ» ብለው የሚመሰክሩለት ሳላህ፣ በምሳሌነት የሚመራ [ይላል] እና ለዝርዝር ነገሮች ከፍተኛ ትኩረት የሚሰጥ ጽኑ ተዋጊ ነው። ዋትፎርድን 5 ለ 0 ባሸነፉበት ጨዋታ ላይ፣ ጨዋታው እንደተጠናቀቀ ግብ ጠባቂውን ቤን ፎስተርን «ፍጹም ቅጣት ምት ቢሆን ኖሮ ወደየትኛው አቅጣጫ ትዘል ነበር?» ብሎ መጠየቁ ለስራው ያለውን ቁርጠኝነት ያሳያል።
በአንፊልድ ቆይታው አንዳንዴ ተስፋ መቁረጥ እና ቁጣ ታይቶበት ያውቃል። ባለፈው ታህሳስ ከዋና አሰልጣኙ አርኔ ስሎት ጋር የነበረው አለመግባባት አሁን ላለው ስንብት መነሻ ሆኗል። ይህ የውድድር ዘመን ለሊቨርፑል ስብስብ እጅግ ከባድ የነበረ ሲሆን፣ የቡድን አጋሩ ዲዮጎ ጆታ ህይወት ማለፍ ሳላህን ክፉኛ ጎድቶታል። «ከእረፍት በኋላ ወደ ሊቨርፑል መመለስ እንደዚህ ያስፈራኛል ብዬ አስቤ አውቅም» ሲል ሀዘኑን ገልጾ፣ በአንፊልድ ፊት እምባውን በማፍሰስ ሰብዓዊነቱን አሳይቷል።
በሜዳ ላይ ግን ሳላህ ከተፈጥሮ በላይ ነበር። በአንፊልድ የመጀመሪያ የውድድር ዘመኑ 58 የጎል ተሳትፎዎችን (በየ 71 ደቂቃው አንድ ጎል ላይ ተሳትፎ) በማድረግ ሜሲ እና ሮናልዶ ካሉበት ደረጃ ደርሷል። ማድሪድ ላይ ቶተንሃምን አሸንፈው የሻምፒዮንስ ሊግ ዋንጫ ሲያነሱ፣ በጉዲሰን ፓርክ ኤቨርተን ላይ የፑስካስ አዋርድ ያሸነፈባትን ጎል ሲያገባ፣ እና በኦልድ ትራፎርድ ማንችስተር ዩናይትድ ላይ ያሳየው ጀብዱ... ትዝታዎቹ ማለቂያ የላቸውም። የሲቲው አይሜሪክ ላፖርት ጭምር «ሳላህ በእኛ ላይ ሁልጊዜ እሳት ይተፋ ነበር፤ ለመከላከል ከገጠሙኝ ከባድ ተጫዋቾች አንዱ ነው» በማለት ይመሰክራል።
ሸሚዙን አውልቆ ደስታውን ሲገልጽም ሆነ በሱጁድ ፈጣሪውን ሲያመሰግን፣ የሳላህ ምስሎች መቼም አይረሱም። የቀድሞው አምበል ስቲቨን ጀራርድ «ቁጥሮቹ፣ ዋንጫዎቹ እና የገነባው ባህል የራሳቸው ታሪክ ይናገራሉ። መሀመድ ሳላህ በሁላችንም ዘንድ የተወደደ የክለቡ እውነተኛ ጀግና ነው» ሲል አወድሶታል። ትሬንት አሌክሳንደር አርኖልድም ለክለቡ ያላቸውን ዋጋ ሲገልጽ ሳላህን እና ጀራርድን በእኩልነት አንደኛ ደረጃ ላይ አስቀምጧቸዋል።
የ2024-25 የውድድር ዘመን ሊቨርፑል 20ኛውን የሊግ ዋንጫ ሲያነሳ፣ ሳላህ ከፍተኛ ጎል እና አሲስት በማድረግ በእንግሊዝ እግር ኳስ ታሪክ ውስጥ ደማቅ አሻራ አሳርፏል። አሁን ግን ሁሉም ነገር ፍጻሜ አለው። ከግብጽ የናይል ዴልታ የተነሳው የዚህ ድንቅ ተዋጊ ጉዞ፣ በሜርሲሳይድ አንፊልድ ላይ የማይረሳ ታሪክ ጽፎ ወደሚቀጥለው ምዕራፍ ተሸጋግሯል። የርገን ክሎፕ እንዳሉት፣ «ሲመጣ ሰዎች ምን እንደሚያስቡ ሳይሆን፣ ሲሄድ ምን እንደሚያስቡ ማወቁ ነው ትልቁ ነገር»። መሀመድ ሳላህ... ለአንፊልድ ትክክለኛው ተዋጊ፣ በትክክለኛው ጊዜ የመጣው ጀግና!
2 months ago
በፕሪሚየር ሊጉ ምርጡ የበላይነት ጊዜ የየትኛው ክለብ ነው?
#ethiopia | ማንቺስተር ዩናይትድ 1995-2001
የሰር አሌክስ ፌርጉሰን የመጀመሪያው ምርጡ ቡድን ነው።ቀያይ ሰይጣናቱ ከመጀመሪያ ዘጠኝ የፕሪሚየር ሊግ ዋንጫዎቻቸው ሰባቱን ያሳኩበት ነው።የ1998-99 የሶስትዮሽ ዋንጫን ያሳኩበት ውድድር አመት ደግሞ በምርጥነቱ የሚነሳው ነው።ግማሽ የሚሆነው የቡድን ስብስብ የተገኘው ደግሞ "ከclass of 92" ነው።እንደ ዴቪድ ቤካም ጋሪ እና ፊል ኔቭል ኒክ በት ሪያን ጊግስ እና ፖል ስኮልስ ያሉት ማለት ነው።
ኤሪክ ካንቶና ፒተር ሽማይክል ሮይ ኪን አንዲ ኮል እና ድዋይት ዮርክ በወቅቱ በቡድኑ ውስጥ የነበሩ ሌሎች ክዋክብት ተጫዋቾች ናቸው።
አርሰናል 2001-2004
የአርሰን ቬንገር አርሰናል የሰር አሌክስ ቡድንን በወጥነት ለሊጉ ዋንጫ ክብር መፎካከር የቻለ የመጀመሪያው ቡድን ነው።በ1997-98 እና 2001-02 የሁለትዮሽ ዋንጫን ክብር ያሳካ ሲሆን በ2003-04 ደግሞ "Invincible" ሆኖ ባለ ክብር ሆኗል።
ከ1999-2005 ስምንት ጊዜ ሁለተኛ ደረጃን በመያዝ አጠናቀዋል።በዚህ ቡድን ውስጥ ፈረንሳውያኑ ኮከቦች ቲዬሪ ሆነሪ ፖትሪክ ቪዬራ እና ሮበርት ፒሬዝ ሆላንዳዊው ጥበበኛ ዴኒስ ቤርካምፕ እንግሊዛውያኑ ተከላካዮች አሽሊ ኮል እና ሶል ካምቤል ከምርጦቹ መካከል ነበሩ።
ቼልሲ 2004-2007
ጆዜ ሞውሪንሆ በሰማያዊዮቹ ቤት በ2004 ከመጡ በኋላ የራሳቸውን ትልቁን አሻራ ማኖር የቻሉት በፍጥነት ነበር።
ራሳቸውን "The Special One" በማለት ለእንግሊዝ ሚዲያ ያስተዋወቁበት መንገድ ትልቁ የመነጋገሪያ ርዕስም ነበር።በመጀመሪያው ዙር ቆይታቸው ሁለት ጊዜ የሊጉን ዋንጫ ሲያነሱ በሶስተኛ የውድድር ዘመን የክለቡ ቆይታቸው ቡድናቸው ሁለተኛ ደረጃን ይዞ አጠናቋል።
በመጀመሪያ የውድድር አመት ቆይታቸው የሊጉን ዋንጫ ሲያሳኩ እስካሁን ያልተሰበሩ በርካታ ሪከርዶችን በመያዝ ነው።
እንግሊዛውያኑ ፍራንክ ላምፓርድ ጆን ቴሪ እና ጆ ኮል ግብ ጠባቂው ፔተር ቼክ የተከላካይ አማካዩ ክሎድ ማኬሌሌ እና አጥቂው ዲዲዬ ድሮግባ ከወርቃማው ቡድን ተጫዋቾች መካከል ዋነኞቹ ነበሩ።
ማንቺስተር ዩናይትድ ከ2006-2011
የፌርጉሰን ሁለተኛው ምርጡ ቡድን ነው።ለሶስት ተከታታይ የውድድር ዘመን የፕሪሚየር ሊጉን ዋንጫ ለማንሳት ከተሳነው በኋላም በአምስት አመት ውስጥ ለአራት ጊዜያት ያህል ባለ ክብር የሆነበት ነው።በ2007-08 ደግሞ የሻምፒየንስ ሊጉን ዋንጫ አሳክቷል።
ክርስቲያኖ ሮናልዶ እና ዌይን ሩኒ ግብ ጠባቂው ኤድዊን ቫንደርሳር አይረሴዎቹ የቡድኑ ቁልፍ ተጫዋቾች ነበሩ።
ማንቺስተር ሲቲ ከ2017-2024
በስተመጨረሻ የአሁኑን የጋርዲዮላ ቡድን እናገኛለን።በቶፕ ዲቪዥን ተከታታይ አራት የሊግ ክብሮችን በማሳካት የመጀመሪያው ቡድን ነው።በ2017- 18 100 ነጥቦችን በቀጣይ አመት ደግሞ 98 መሰብሰብ ችሏል። በ2022-23 የውድድር ዘመን የሶስትዮሽ ዋንጫን ክብር አሳክቷል። በዚህ ጊዜ የሲቲን የበላይነት ለመፈተን ጥረት ያደረገው ቡድን የየርገን ክሎፕ ሊቨርፑል ብቻ ነው ብሎ ማንሳት ይቻላል።
ኬቨን ዴብሩይነ ኤደርሰን በርናንዶ ሲልቫ ካይል ዎከር በልዩነት በዚህ ስኬታማ ጊዜ ውስጥ ስማቸው በትልቁ የሚነሳ ተጫዋቾች ናቸው።
(በሳምሶን አበበ)
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#ethiopia | ማንቺስተር ዩናይትድ 1995-2001
የሰር አሌክስ ፌርጉሰን የመጀመሪያው ምርጡ ቡድን ነው።ቀያይ ሰይጣናቱ ከመጀመሪያ ዘጠኝ የፕሪሚየር ሊግ ዋንጫዎቻቸው ሰባቱን ያሳኩበት ነው።የ1998-99 የሶስትዮሽ ዋንጫን ያሳኩበት ውድድር አመት ደግሞ በምርጥነቱ የሚነሳው ነው።ግማሽ የሚሆነው የቡድን ስብስብ የተገኘው ደግሞ "ከclass of 92" ነው።እንደ ዴቪድ ቤካም ጋሪ እና ፊል ኔቭል ኒክ በት ሪያን ጊግስ እና ፖል ስኮልስ ያሉት ማለት ነው።
ኤሪክ ካንቶና ፒተር ሽማይክል ሮይ ኪን አንዲ ኮል እና ድዋይት ዮርክ በወቅቱ በቡድኑ ውስጥ የነበሩ ሌሎች ክዋክብት ተጫዋቾች ናቸው።
አርሰናል 2001-2004
የአርሰን ቬንገር አርሰናል የሰር አሌክስ ቡድንን በወጥነት ለሊጉ ዋንጫ ክብር መፎካከር የቻለ የመጀመሪያው ቡድን ነው።በ1997-98 እና 2001-02 የሁለትዮሽ ዋንጫን ክብር ያሳካ ሲሆን በ2003-04 ደግሞ "Invincible" ሆኖ ባለ ክብር ሆኗል።
ከ1999-2005 ስምንት ጊዜ ሁለተኛ ደረጃን በመያዝ አጠናቀዋል።በዚህ ቡድን ውስጥ ፈረንሳውያኑ ኮከቦች ቲዬሪ ሆነሪ ፖትሪክ ቪዬራ እና ሮበርት ፒሬዝ ሆላንዳዊው ጥበበኛ ዴኒስ ቤርካምፕ እንግሊዛውያኑ ተከላካዮች አሽሊ ኮል እና ሶል ካምቤል ከምርጦቹ መካከል ነበሩ።
ቼልሲ 2004-2007
ጆዜ ሞውሪንሆ በሰማያዊዮቹ ቤት በ2004 ከመጡ በኋላ የራሳቸውን ትልቁን አሻራ ማኖር የቻሉት በፍጥነት ነበር።
ራሳቸውን "The Special One" በማለት ለእንግሊዝ ሚዲያ ያስተዋወቁበት መንገድ ትልቁ የመነጋገሪያ ርዕስም ነበር።በመጀመሪያው ዙር ቆይታቸው ሁለት ጊዜ የሊጉን ዋንጫ ሲያነሱ በሶስተኛ የውድድር ዘመን የክለቡ ቆይታቸው ቡድናቸው ሁለተኛ ደረጃን ይዞ አጠናቋል።
በመጀመሪያ የውድድር አመት ቆይታቸው የሊጉን ዋንጫ ሲያሳኩ እስካሁን ያልተሰበሩ በርካታ ሪከርዶችን በመያዝ ነው።
እንግሊዛውያኑ ፍራንክ ላምፓርድ ጆን ቴሪ እና ጆ ኮል ግብ ጠባቂው ፔተር ቼክ የተከላካይ አማካዩ ክሎድ ማኬሌሌ እና አጥቂው ዲዲዬ ድሮግባ ከወርቃማው ቡድን ተጫዋቾች መካከል ዋነኞቹ ነበሩ።
ማንቺስተር ዩናይትድ ከ2006-2011
የፌርጉሰን ሁለተኛው ምርጡ ቡድን ነው።ለሶስት ተከታታይ የውድድር ዘመን የፕሪሚየር ሊጉን ዋንጫ ለማንሳት ከተሳነው በኋላም በአምስት አመት ውስጥ ለአራት ጊዜያት ያህል ባለ ክብር የሆነበት ነው።በ2007-08 ደግሞ የሻምፒየንስ ሊጉን ዋንጫ አሳክቷል።
ክርስቲያኖ ሮናልዶ እና ዌይን ሩኒ ግብ ጠባቂው ኤድዊን ቫንደርሳር አይረሴዎቹ የቡድኑ ቁልፍ ተጫዋቾች ነበሩ።
ማንቺስተር ሲቲ ከ2017-2024
በስተመጨረሻ የአሁኑን የጋርዲዮላ ቡድን እናገኛለን።በቶፕ ዲቪዥን ተከታታይ አራት የሊግ ክብሮችን በማሳካት የመጀመሪያው ቡድን ነው።በ2017- 18 100 ነጥቦችን በቀጣይ አመት ደግሞ 98 መሰብሰብ ችሏል። በ2022-23 የውድድር ዘመን የሶስትዮሽ ዋንጫን ክብር አሳክቷል። በዚህ ጊዜ የሲቲን የበላይነት ለመፈተን ጥረት ያደረገው ቡድን የየርገን ክሎፕ ሊቨርፑል ብቻ ነው ብሎ ማንሳት ይቻላል።
ኬቨን ዴብሩይነ ኤደርሰን በርናንዶ ሲልቫ ካይል ዎከር በልዩነት በዚህ ስኬታማ ጊዜ ውስጥ ስማቸው በትልቁ የሚነሳ ተጫዋቾች ናቸው።
(በሳምሶን አበበ)
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
2 months ago
የራሱን ታሪክ የደገመው አርሰናል…
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 14፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) አርሰናል በስፔናዊው አሰልጣኝ ሚኬል አርቴታ እየተመራ የ2025/26 የውድድር ዓመት የሊጉ ሻምፒዮን መሆኑ ይታወቃል፡፡
ባለፉት ሦስት የውድድር ዓመታት በሊጉ ሁለተኛ ደረጃን ይዞ ያጠናቀቀው አርሰናል በዚህ ዓመት ሻምፒዮን በመሆን ከዚህ ቀደም ራሱ ፅፎት የነበረውን ታሪክ መድገም ችሏል፡፡
የሰሜን ለንደኑ ክለብ በ2022/23 እና በ2023/24 ማንቼስተር ሲቲን እንዲሁም አምና ሊቨርፑልን በመከተል በሁለተኛነት ማጠናቀቁ ይታወሳል፡፡
ከዚህ ቀደም አርሰናል በአሰልጣኝ አርሰን ቬንገር እየተመራ ለተከታታይ ሦስት የውድድር ዓመት 2ኛ ሆኖ ከጨረሰ በኋላ በአራተኛው የሊጉ ሻምፒዮን ሆኖ እንደነበር ይታወሳል፡፡
ከ1998/99 እስከ 2000/01 የውድድር ዓመት ድረስ ማንቼስተር ዩናይትድ ለተከታታይ ሦስት የውድድር ዓመት የሊጉ ሻምፒዮን ሲሆን አርሰናል 2ኛ ደረጃን ይዞ ማጠናቀቁ አይዘነጋም፡፡
በወቅቱ ለተከታታይ ሦስት የውድድር ዓመታት 2ኛ ደረጃን ይዞ ካጠናቀቀ በኋላ በአራተኛው የውድድር ዓመት (በ2001/02) የሊጉ ሻምፒዮን መሆን ችሏል፡፡
በወቅቱ አርሰናል ካደረጋቸው 38 ጨዋታዎች በ26ቱ አሸንፎ፣ 9 ጊዜ አቻ የተለያየ ሲሆን 3 ሽንፈት አስተናግዶ 87 ነጥብ በመሰብሰብ ነበር ሻምፒዮን የሆነው፡፡
መድፈኞቹ በስፔናዊው አሰልጣኝ ሚኬል አርቴታ እየተመሩ በዚህ ዓመት ያሳኩት የሊጉ ክብር በቀድሞው አሰልጣኛቸው አርሰን ቬንገር እየተመሩ ካሳኩት የሊጉ ዋንጫ ጋር አስገራሚ የታሪክ ግጥምጥሞሽ ፈጥሯል፡፡
አሰልጣኝ ሚኬል አርቴታ ባለፉት ሦስት ዓመታት ከመድፈኞቹ ጋር ዋንጫውን ማሳካት ባይችሉም የቀደሙት ዘመናት ታላቅነቱን በማይመጥን ሁኔታ ከዋንጫ ፉክክር ርቆ የቆየውን ክለብ ወደ ተፎካካሪነት በመመለስ ትልቅ ሥራ ሰርተዋል፡፡
በዚህ የውድድር ዓመት አንድ ጨዋታ እየቀረው ሻምፒዮን መሆኑን ያረጋገጠው አርሰናል ካደረጋቸው 37 ጨዋታዎች 25 ድል፣ 7 አቻ እና 5 ሽንፈት አስመዝግቧል፡፡
ሻምፒዮኑ አርሰናል የመጨረሻ ሳምንት ጨዋታውን የሚያሸንፍ ከሆነ በ2001/02 የውድድር ዓመት የሊጉ ሻምፒዮን ሲሆን ካሸነፈው 26 ጨዋታ ጋር በተመሳሳይ 26ኛ የሊግ ጨዋታ ድሉ ይሆናል፡፡
አርቴታ አርሰናልን ሲረከብ ቡድኑ ከሊጉ ዋንጫ መራቅ ብቻ ሳይሆን በአውሮፓ መድረክ የሚያሳትፈውን ቦታ ይዞ ለማጠናቀቅ የሚቸገር ቡድን ነበር፡፡
በአሰልጣኝ ሚኬል አርቴታ የቡድን ግንባታ ሒደት ከ22 ዓመታት በኋላ ከሊጉ ዋንጫ ጋር የተገናኙት መድፈኞቹ የፊታችን እሁድ ዋንጫውን በክብር ይቀበላሉ፡፡
በወንድማገኝ ጸጋዬ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 14፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) አርሰናል በስፔናዊው አሰልጣኝ ሚኬል አርቴታ እየተመራ የ2025/26 የውድድር ዓመት የሊጉ ሻምፒዮን መሆኑ ይታወቃል፡፡
ባለፉት ሦስት የውድድር ዓመታት በሊጉ ሁለተኛ ደረጃን ይዞ ያጠናቀቀው አርሰናል በዚህ ዓመት ሻምፒዮን በመሆን ከዚህ ቀደም ራሱ ፅፎት የነበረውን ታሪክ መድገም ችሏል፡፡
የሰሜን ለንደኑ ክለብ በ2022/23 እና በ2023/24 ማንቼስተር ሲቲን እንዲሁም አምና ሊቨርፑልን በመከተል በሁለተኛነት ማጠናቀቁ ይታወሳል፡፡
ከዚህ ቀደም አርሰናል በአሰልጣኝ አርሰን ቬንገር እየተመራ ለተከታታይ ሦስት የውድድር ዓመት 2ኛ ሆኖ ከጨረሰ በኋላ በአራተኛው የሊጉ ሻምፒዮን ሆኖ እንደነበር ይታወሳል፡፡
ከ1998/99 እስከ 2000/01 የውድድር ዓመት ድረስ ማንቼስተር ዩናይትድ ለተከታታይ ሦስት የውድድር ዓመት የሊጉ ሻምፒዮን ሲሆን አርሰናል 2ኛ ደረጃን ይዞ ማጠናቀቁ አይዘነጋም፡፡
በወቅቱ ለተከታታይ ሦስት የውድድር ዓመታት 2ኛ ደረጃን ይዞ ካጠናቀቀ በኋላ በአራተኛው የውድድር ዓመት (በ2001/02) የሊጉ ሻምፒዮን መሆን ችሏል፡፡
በወቅቱ አርሰናል ካደረጋቸው 38 ጨዋታዎች በ26ቱ አሸንፎ፣ 9 ጊዜ አቻ የተለያየ ሲሆን 3 ሽንፈት አስተናግዶ 87 ነጥብ በመሰብሰብ ነበር ሻምፒዮን የሆነው፡፡
መድፈኞቹ በስፔናዊው አሰልጣኝ ሚኬል አርቴታ እየተመሩ በዚህ ዓመት ያሳኩት የሊጉ ክብር በቀድሞው አሰልጣኛቸው አርሰን ቬንገር እየተመሩ ካሳኩት የሊጉ ዋንጫ ጋር አስገራሚ የታሪክ ግጥምጥሞሽ ፈጥሯል፡፡
አሰልጣኝ ሚኬል አርቴታ ባለፉት ሦስት ዓመታት ከመድፈኞቹ ጋር ዋንጫውን ማሳካት ባይችሉም የቀደሙት ዘመናት ታላቅነቱን በማይመጥን ሁኔታ ከዋንጫ ፉክክር ርቆ የቆየውን ክለብ ወደ ተፎካካሪነት በመመለስ ትልቅ ሥራ ሰርተዋል፡፡
በዚህ የውድድር ዓመት አንድ ጨዋታ እየቀረው ሻምፒዮን መሆኑን ያረጋገጠው አርሰናል ካደረጋቸው 37 ጨዋታዎች 25 ድል፣ 7 አቻ እና 5 ሽንፈት አስመዝግቧል፡፡
ሻምፒዮኑ አርሰናል የመጨረሻ ሳምንት ጨዋታውን የሚያሸንፍ ከሆነ በ2001/02 የውድድር ዓመት የሊጉ ሻምፒዮን ሲሆን ካሸነፈው 26 ጨዋታ ጋር በተመሳሳይ 26ኛ የሊግ ጨዋታ ድሉ ይሆናል፡፡
አርቴታ አርሰናልን ሲረከብ ቡድኑ ከሊጉ ዋንጫ መራቅ ብቻ ሳይሆን በአውሮፓ መድረክ የሚያሳትፈውን ቦታ ይዞ ለማጠናቀቅ የሚቸገር ቡድን ነበር፡፡
በአሰልጣኝ ሚኬል አርቴታ የቡድን ግንባታ ሒደት ከ22 ዓመታት በኋላ ከሊጉ ዋንጫ ጋር የተገናኙት መድፈኞቹ የፊታችን እሁድ ዋንጫውን በክብር ይቀበላሉ፡፡
በወንድማገኝ ጸጋዬ
Sponsored by
Surafel
2 months ago
(ዘ-ሐበሻ ስፖርት) የሳዑዲ አረቢያ እግር ኳስን በዓለም መድረክ ላይ ላስተዋወቀው የሊጉ "ፖስተር ቦይ" ከዚህ የተሻለ የድል ምስል ሊኖር አይችልም፦ ክርስቲያኖ ሮናልዶ የሳዑዲ ፕሮ ሊግን ዋንጫ ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ ላይ ከፍ አድርጎ አነሳው!
አል-ናስር በታህሳስ 2022 የማንቸስተር ዩናይትድን መልቀቅ ተከትሎ ይህንን ሜጋ ስታር ወደ ሪያድ ሲያመጣው፣ ዓለምን ማስደንገጥ እና ሀገሪቱን ወደ ዓለም አቀፉ የስፖርት መድረክ ማሸጋገር ዋነኛ ዓላማው ነበር። ይሁን እንጂ፣ ከሦስት ዓመታት በላይ ቆይታ በኋላ፣ ይህ የ41 ዓመቱ የእግር ኳስ ጠበብት አንድም ትልቅ የሀገር ውስጥ ዋንጫ አለማንሳቱ ብዙዎችን ሲያስገርም ቆይቷል።
የረዥም ጊዜ ጥበቃው ግን ሐሙስ ምሽት ማብቂያ አግኝቷል። በውድድር ዘመኑ የመጨረሻ ቀን፣ አል-ናስር ዳማክን 4ለ1 በረመረመበት አጓጊ ጨዋታ ላይ ሮናልዶ ሁለት ግቦችን በማስቆጠር፣ የዘመናት ባላንጣ የሆነውን አል-ሂላልን በመርታት ክለቡ ከ2019 ወዲህ ለመጀመሪያ ጊዜ የሻምፒዮንነት ክብሩን እንዲቀዳጅ አስችሎታል።
በቅርቡ በሳዑዲ ፕሮ ሊግ 100ኛ ግቡን ያስቆጠረው ሮናልዶ፣ በሁሉም ውድድሮች ለአል-ናስር 129 ግቦችን መረብ ላይ አሳርፏል። ይህ ዋንጫ ግን፣ እሱ በዋናነት እንዲያነሳው የተፈረመበት ትልቁ የክብር አክሊል ነበር።
ሮናልዶ ከሦስት ዓመት ተኩል በፊት ወደ ሳዑዲ ካመራ በኋላ ብዙ ነገሮች ተለውጠዋል። የእሱ መምጣት እንደ ካሪም ቤንዜማ፣ ንጎሎ ካንቴ፣ ሪያድ ማህሬዝ፣ ሳዲዮ ማኔ፣ ኔይማር እና ሌሎችም ታላላቅ ከዋክብት ወደ 'ታላላቆቹ አራት' ክለቦች (በሪያድ አል-ሂላል እና አል-ናስር፣ በጅዳ አል-አህሊ እና አል-ኢትሃድ) እንዲጎርፉ መንገድ ጠርጓል።
በ2023 ክረምት ላይ እነዚህ አራት ክለቦች በሀገሪቱ የህዝብ ኢንቨስትመንት ፈንድ (PIF) ስር የገቡ ሲሆን፣ በሚያዝያ 2026 ግን የ70 በመቶ የአል-ሂላል ድርሻ በልዑል አልዋሊድ ቢን ታላል ለሚመራው 'ኪንግደም ሆልዲንግ ኩባንያ' መሸጡ ይታወሳል።
ይህኛው የውድድር ዘመን ግን ከሁሉም የተለየ እና እጅግ አጓጊ ነበር። ለተወሰነ ጊዜ አራት ቡድኖች በዋንጫ ፉክክሩ ውስጥ ነበሩ። በአይቫን ቶኒ ግቦች የታገዘው አል-አህሊ፣ እና በሳዑዲው የነዳጅ ግዙፍ ኩባንያ አራምኮ የሚደገፈውና በብሬንዳን ሮጀርስ የሚሰለጥነው አል-ቃድሲያህ በመጨረሻዎቹ ሳምንታት ከፉክክሩ ርቀዋል።
ፉክክሩ በአል-ናስር እና በአል-ሂላል መካከል ብቻ ተወስኖ የቀጠለ ሲሆን፣ ሜይ 12 የተካሄደው የሁለቱ ክለቦች ትልቁ ፍጥጫ የሊጉን አቅጣጫ የወሰነ ነበር። ከ180 በላይ ሀገራት የተላለፈው ይህ ታሪካዊ ጨዋታ፣ አስገራሚ ፍጻሜ ነበረው። አል-ናስር 1ለ0 እየመራ ጨዋታው 97ኛው ደቂቃ ላይ ሲደርስ፣ ቢጫ የለበሱ ደጋፊዎች ድሉን ማክበር ጀምረው ነበር። ነገር ግን በመጨረሻዋ ሰከንድ ላይ ግብ ጠባቂው ቤንቶ በቀላሉ ሊይዛት የሚገባትን ኳስ አምልጦት በራሱ ላይ ባስቆጠረው ግብ ጨዋታው 1ለ1 ተጠናቀቀ። የዋንጫው ፉክክር ህያው ሆኖ ቢቀጥልም፣ ሐሙስ ዕለት ግን አል-ናስር ስራውን በተጨባጭ አጠናቋል።
ይህ ድል ለአል-ናስር 11ኛው የሊግ ዋንጫ ሲሆን፣ ለክርስቲያኖ ሮናልዶ ደግሞ በእንግሊዝ (ማንቸስተር ዩናይትድ)፣ በስፔን (ሪያል ማድሪድ) እና በጣሊያን (ጁቬንቱስ) ካነሳቸው ዋንጫዎች በመቀጠል 8ኛው የሊግ ሻምፒዮንነት ሆኖ ተመዝግቧል።
"በሪያድ ያሉ ባለስልጣናት የአል-ናስርን ድል የሮናልዶን ዝውውር እና ክለቡን በPIF ስር ለማቆየት የተደረገውን ውሳኔ ትክክለኛነት እንደሚያረጋግጥ አድርገው ይመለከቱታል" ሲሉ በፓሪስ ኢምሊዮን ቢዝነስ ስር የአፍሮ-ዩራሲያ ስፖርት ፕሮፌሰር የሆኑት ሳይመን ቻድዊክ ለቢቢሲ ተናግረዋል።
ይህ የሊግ ድል የመጣው፣ ቅዳሜ ዕለት የእስያ ዩሮፓ ሊግ አቻ በሆነው 'ኤኤፍሲ ቻምፒየንስ ሊግ 2' ፍጻሜ ላይ አል-ናስር ባልተጠበቀ ሁኔታ በጃፓኑ ጋምባ ኦሳካ ከተሸነፈ በኋላ በመሆኑ፣ ለሮናልዶ ትልቅ እፎይታን ሰጥቶታል።
የዘንድሮው የውድድር ዘመን ከውዝግብ የጸዳ አልነበረም። በየካቲት ወር ሮናልዶ በሁለት የሊግ ጨዋታዎች ላይ ያልተሰለፈ ሲሆን፣ ይህ የሆነው PIF ክለቡን የሚያስተዳድርበት መንገድ ከአል-ሂላል ጋር ሲነጻጸር ፍትሃዊ አይደለም በሚል ቅሬታ እንደሆነ ተዘግቧል። በሌላ በኩል ደግሞ ሊጉ ሮናልዶን ይደግፋል የሚሉ ወገኖች አልጠፉም። የአል-አህሊው አይቫን ቶኒ እና ብራዚላዊው ጋሌኖ ሊጉ ለሮናልዶ እና ለአል-ናስር ያደላል ሲሉ ከከሰሱት መካከል ይገኛሉ።
ሮናልዶ ለዚህ በሰጠው ምላሽ፡ "ይህ ለሊጉ ጥሩ አይመስለኝም። ሁሉም ያማርራል። ይህ እግር ኳስ እንጂ ጦርነት አይደለም... ግን ሁሉም ነገር አይፈቀድም። ብዙ፣ ብዙ መጥፎ ነገሮችን ስላየሁ በውድድር ዘመኑ መጨረሻ ላይ እናገራለሁ። ብዙ ተጫዋቾች በኢንስታግራም እና ፌስቡክ ላይ ስለ ዳኞች፣ ስለ ሊጉ እና ስለ ፕሮጀክቱ ቅሬታ ያሰማሉ። ይህ ጥሩ አይደለም፤ የሊጉም ዓላማ ይህ አይደለም" በማለት ተችቷል።
በአጠቃላይ የሳዑዲ አረቢያ የስፖርት ፕሮጀክት በቅርቡ ጥያቄ ውስጥ ወድቋል። ሚያዝያ ላይ PIF የሊቭ ጎልፍ የገንዘብ ድጋፍን እንደሚያቋርጥ ሲያሳውቅ፣ በጥር ወር ደግሞ ሀገሪቱ ልታስተናግደው የነበረው የ2029 የክረምት የእስያ ጨዋታዎች ላልተወሰነ ጊዜ ተራዝሟል። የሴቶች ቴኒስ የፍጻሜ ውድድርም ከሳዑዲ እንደሚወጣ ተዘግቧል።
በእግር ኳሱም ቢሆን ሚዲያው በታላላቅ ተጫዋቾች ዝውውር ወሬ ይሞላበት የነበረው ጊዜ ያለፈ ይመስላል። አሁንም ቢሆን አል-ቃድሲያህ ጣሊያናዊውን ማቴዎ ሬቴጉዊን በ57 ሚሊዮን ፓውንድ፣ አል-ሂላል ደግሞ ዳርዊን ኑኔዝን በ46 ሚሊዮን ፓውንድ ማስፈረማቸው ትልቅ እርምጃ ቢሆንም፣ ከ2023ቱ የዝውውር ማዕበል ጋር ሲነጻጸር አሁን ትኩረቱ ዳግም ሊሸጡ በሚችሉ ወጣት ተጫዋቾች ላይ ሆኗል። ይሁን እንጂ፣ ሊቨርፑልን የሚለቀቀውን ሞሀመድ ሳላህን የመሰለ አንጋፋ ኮከብ ለማምጣት አሁንም በጀቱ ክፍት መሆኑ ይነገራል።
የሮናልዶ የሊግ ሻምፒዮንነት የሳዑዲ ክለቦች በአንድ የዝውውር መስኮት 700 ሚሊዮን ፓውንድ ያፈሱበት "ያለፈው ወርቃማ ዘመን የመጨረሻው የድል ጩኸት" ተደርጎ ሊወሰድ ይችላል። ቀጣዩ የሳዑዲ እግር ኳስ እርምጃ ምን ሊሆን እንደሚችል የጊዜ ጉዳይ ቢሆንም፣ ለአሁኑ ግን የሪያድ ቢጫ ለባሾች እና የዓለም አቀፉ የሮናልዶ ደጋፊዎች በደስታ ማዕበል ውስጥ እየዋኙ ይገኛሉ።
አል-ናስር በታህሳስ 2022 የማንቸስተር ዩናይትድን መልቀቅ ተከትሎ ይህንን ሜጋ ስታር ወደ ሪያድ ሲያመጣው፣ ዓለምን ማስደንገጥ እና ሀገሪቱን ወደ ዓለም አቀፉ የስፖርት መድረክ ማሸጋገር ዋነኛ ዓላማው ነበር። ይሁን እንጂ፣ ከሦስት ዓመታት በላይ ቆይታ በኋላ፣ ይህ የ41 ዓመቱ የእግር ኳስ ጠበብት አንድም ትልቅ የሀገር ውስጥ ዋንጫ አለማንሳቱ ብዙዎችን ሲያስገርም ቆይቷል።
የረዥም ጊዜ ጥበቃው ግን ሐሙስ ምሽት ማብቂያ አግኝቷል። በውድድር ዘመኑ የመጨረሻ ቀን፣ አል-ናስር ዳማክን 4ለ1 በረመረመበት አጓጊ ጨዋታ ላይ ሮናልዶ ሁለት ግቦችን በማስቆጠር፣ የዘመናት ባላንጣ የሆነውን አል-ሂላልን በመርታት ክለቡ ከ2019 ወዲህ ለመጀመሪያ ጊዜ የሻምፒዮንነት ክብሩን እንዲቀዳጅ አስችሎታል።
በቅርቡ በሳዑዲ ፕሮ ሊግ 100ኛ ግቡን ያስቆጠረው ሮናልዶ፣ በሁሉም ውድድሮች ለአል-ናስር 129 ግቦችን መረብ ላይ አሳርፏል። ይህ ዋንጫ ግን፣ እሱ በዋናነት እንዲያነሳው የተፈረመበት ትልቁ የክብር አክሊል ነበር።
ሮናልዶ ከሦስት ዓመት ተኩል በፊት ወደ ሳዑዲ ካመራ በኋላ ብዙ ነገሮች ተለውጠዋል። የእሱ መምጣት እንደ ካሪም ቤንዜማ፣ ንጎሎ ካንቴ፣ ሪያድ ማህሬዝ፣ ሳዲዮ ማኔ፣ ኔይማር እና ሌሎችም ታላላቅ ከዋክብት ወደ 'ታላላቆቹ አራት' ክለቦች (በሪያድ አል-ሂላል እና አል-ናስር፣ በጅዳ አል-አህሊ እና አል-ኢትሃድ) እንዲጎርፉ መንገድ ጠርጓል።
በ2023 ክረምት ላይ እነዚህ አራት ክለቦች በሀገሪቱ የህዝብ ኢንቨስትመንት ፈንድ (PIF) ስር የገቡ ሲሆን፣ በሚያዝያ 2026 ግን የ70 በመቶ የአል-ሂላል ድርሻ በልዑል አልዋሊድ ቢን ታላል ለሚመራው 'ኪንግደም ሆልዲንግ ኩባንያ' መሸጡ ይታወሳል።
ይህኛው የውድድር ዘመን ግን ከሁሉም የተለየ እና እጅግ አጓጊ ነበር። ለተወሰነ ጊዜ አራት ቡድኖች በዋንጫ ፉክክሩ ውስጥ ነበሩ። በአይቫን ቶኒ ግቦች የታገዘው አል-አህሊ፣ እና በሳዑዲው የነዳጅ ግዙፍ ኩባንያ አራምኮ የሚደገፈውና በብሬንዳን ሮጀርስ የሚሰለጥነው አል-ቃድሲያህ በመጨረሻዎቹ ሳምንታት ከፉክክሩ ርቀዋል።
ፉክክሩ በአል-ናስር እና በአል-ሂላል መካከል ብቻ ተወስኖ የቀጠለ ሲሆን፣ ሜይ 12 የተካሄደው የሁለቱ ክለቦች ትልቁ ፍጥጫ የሊጉን አቅጣጫ የወሰነ ነበር። ከ180 በላይ ሀገራት የተላለፈው ይህ ታሪካዊ ጨዋታ፣ አስገራሚ ፍጻሜ ነበረው። አል-ናስር 1ለ0 እየመራ ጨዋታው 97ኛው ደቂቃ ላይ ሲደርስ፣ ቢጫ የለበሱ ደጋፊዎች ድሉን ማክበር ጀምረው ነበር። ነገር ግን በመጨረሻዋ ሰከንድ ላይ ግብ ጠባቂው ቤንቶ በቀላሉ ሊይዛት የሚገባትን ኳስ አምልጦት በራሱ ላይ ባስቆጠረው ግብ ጨዋታው 1ለ1 ተጠናቀቀ። የዋንጫው ፉክክር ህያው ሆኖ ቢቀጥልም፣ ሐሙስ ዕለት ግን አል-ናስር ስራውን በተጨባጭ አጠናቋል።
ይህ ድል ለአል-ናስር 11ኛው የሊግ ዋንጫ ሲሆን፣ ለክርስቲያኖ ሮናልዶ ደግሞ በእንግሊዝ (ማንቸስተር ዩናይትድ)፣ በስፔን (ሪያል ማድሪድ) እና በጣሊያን (ጁቬንቱስ) ካነሳቸው ዋንጫዎች በመቀጠል 8ኛው የሊግ ሻምፒዮንነት ሆኖ ተመዝግቧል።
"በሪያድ ያሉ ባለስልጣናት የአል-ናስርን ድል የሮናልዶን ዝውውር እና ክለቡን በPIF ስር ለማቆየት የተደረገውን ውሳኔ ትክክለኛነት እንደሚያረጋግጥ አድርገው ይመለከቱታል" ሲሉ በፓሪስ ኢምሊዮን ቢዝነስ ስር የአፍሮ-ዩራሲያ ስፖርት ፕሮፌሰር የሆኑት ሳይመን ቻድዊክ ለቢቢሲ ተናግረዋል።
ይህ የሊግ ድል የመጣው፣ ቅዳሜ ዕለት የእስያ ዩሮፓ ሊግ አቻ በሆነው 'ኤኤፍሲ ቻምፒየንስ ሊግ 2' ፍጻሜ ላይ አል-ናስር ባልተጠበቀ ሁኔታ በጃፓኑ ጋምባ ኦሳካ ከተሸነፈ በኋላ በመሆኑ፣ ለሮናልዶ ትልቅ እፎይታን ሰጥቶታል።
የዘንድሮው የውድድር ዘመን ከውዝግብ የጸዳ አልነበረም። በየካቲት ወር ሮናልዶ በሁለት የሊግ ጨዋታዎች ላይ ያልተሰለፈ ሲሆን፣ ይህ የሆነው PIF ክለቡን የሚያስተዳድርበት መንገድ ከአል-ሂላል ጋር ሲነጻጸር ፍትሃዊ አይደለም በሚል ቅሬታ እንደሆነ ተዘግቧል። በሌላ በኩል ደግሞ ሊጉ ሮናልዶን ይደግፋል የሚሉ ወገኖች አልጠፉም። የአል-አህሊው አይቫን ቶኒ እና ብራዚላዊው ጋሌኖ ሊጉ ለሮናልዶ እና ለአል-ናስር ያደላል ሲሉ ከከሰሱት መካከል ይገኛሉ።
ሮናልዶ ለዚህ በሰጠው ምላሽ፡ "ይህ ለሊጉ ጥሩ አይመስለኝም። ሁሉም ያማርራል። ይህ እግር ኳስ እንጂ ጦርነት አይደለም... ግን ሁሉም ነገር አይፈቀድም። ብዙ፣ ብዙ መጥፎ ነገሮችን ስላየሁ በውድድር ዘመኑ መጨረሻ ላይ እናገራለሁ። ብዙ ተጫዋቾች በኢንስታግራም እና ፌስቡክ ላይ ስለ ዳኞች፣ ስለ ሊጉ እና ስለ ፕሮጀክቱ ቅሬታ ያሰማሉ። ይህ ጥሩ አይደለም፤ የሊጉም ዓላማ ይህ አይደለም" በማለት ተችቷል።
በአጠቃላይ የሳዑዲ አረቢያ የስፖርት ፕሮጀክት በቅርቡ ጥያቄ ውስጥ ወድቋል። ሚያዝያ ላይ PIF የሊቭ ጎልፍ የገንዘብ ድጋፍን እንደሚያቋርጥ ሲያሳውቅ፣ በጥር ወር ደግሞ ሀገሪቱ ልታስተናግደው የነበረው የ2029 የክረምት የእስያ ጨዋታዎች ላልተወሰነ ጊዜ ተራዝሟል። የሴቶች ቴኒስ የፍጻሜ ውድድርም ከሳዑዲ እንደሚወጣ ተዘግቧል።
በእግር ኳሱም ቢሆን ሚዲያው በታላላቅ ተጫዋቾች ዝውውር ወሬ ይሞላበት የነበረው ጊዜ ያለፈ ይመስላል። አሁንም ቢሆን አል-ቃድሲያህ ጣሊያናዊውን ማቴዎ ሬቴጉዊን በ57 ሚሊዮን ፓውንድ፣ አል-ሂላል ደግሞ ዳርዊን ኑኔዝን በ46 ሚሊዮን ፓውንድ ማስፈረማቸው ትልቅ እርምጃ ቢሆንም፣ ከ2023ቱ የዝውውር ማዕበል ጋር ሲነጻጸር አሁን ትኩረቱ ዳግም ሊሸጡ በሚችሉ ወጣት ተጫዋቾች ላይ ሆኗል። ይሁን እንጂ፣ ሊቨርፑልን የሚለቀቀውን ሞሀመድ ሳላህን የመሰለ አንጋፋ ኮከብ ለማምጣት አሁንም በጀቱ ክፍት መሆኑ ይነገራል።
የሮናልዶ የሊግ ሻምፒዮንነት የሳዑዲ ክለቦች በአንድ የዝውውር መስኮት 700 ሚሊዮን ፓውንድ ያፈሱበት "ያለፈው ወርቃማ ዘመን የመጨረሻው የድል ጩኸት" ተደርጎ ሊወሰድ ይችላል። ቀጣዩ የሳዑዲ እግር ኳስ እርምጃ ምን ሊሆን እንደሚችል የጊዜ ጉዳይ ቢሆንም፣ ለአሁኑ ግን የሪያድ ቢጫ ለባሾች እና የዓለም አቀፉ የሮናልዶ ደጋፊዎች በደስታ ማዕበል ውስጥ እየዋኙ ይገኛሉ።
3 months ago
አስቶን ቪላ ሊቨርፑልን በመርታት የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ውድድር ተሳትፎውን ማረጋገጥ ቻለ
#ethiopia | በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የ37ኛ ሳምንት መርሃ ግብር አስቶን ቪላ ሊቨርፑልን 4 ለ 2 በሆነ ውጤት አሸንፏል።
በቪላ ፓርክ ስታዲየም በተካሄደው በዚህ ጨዋታ ኦሊ ዋትኪንስ ሁለት ግቦችን ለአስቶን ቪላ ማስቆጠር የቻለ ሲሆን ሞርጋን ሮጀርስ እና ጆን ማክጊን ደግሞ ቀሪዎቹን ሁለት ጎሎች አክለዋል።
በአንጻሩ ለሊቨርፑል ሁለቱንም ግቦች ከመረብ ያሳረፈው ተከላካዩ ቨርጅል ቫን ዳይክ ነው።
በዚህ ጨዋታ ወሳኝ ሶስት ነጥብ ማግኘት የቻለው አስቶን ቪላ አጠቃላይ የነጥብ መጠኑን 62 በማድረስ በቀጣዩ የውድድር ዘመን በአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ መሳተፉን በይፋ አረጋግጧል።
#astonvilla #liverpool #epl #championsleague #footballnews #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የ37ኛ ሳምንት መርሃ ግብር አስቶን ቪላ ሊቨርፑልን 4 ለ 2 በሆነ ውጤት አሸንፏል።
በቪላ ፓርክ ስታዲየም በተካሄደው በዚህ ጨዋታ ኦሊ ዋትኪንስ ሁለት ግቦችን ለአስቶን ቪላ ማስቆጠር የቻለ ሲሆን ሞርጋን ሮጀርስ እና ጆን ማክጊን ደግሞ ቀሪዎቹን ሁለት ጎሎች አክለዋል።
በአንጻሩ ለሊቨርፑል ሁለቱንም ግቦች ከመረብ ያሳረፈው ተከላካዩ ቨርጅል ቫን ዳይክ ነው።
በዚህ ጨዋታ ወሳኝ ሶስት ነጥብ ማግኘት የቻለው አስቶን ቪላ አጠቃላይ የነጥብ መጠኑን 62 በማድረስ በቀጣዩ የውድድር ዘመን በአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ መሳተፉን በይፋ አረጋግጧል።
#astonvilla #liverpool #epl #championsleague #footballnews #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
3 months ago
ማንቼስተር ሲቲ ወይስ ቼልሲ - ተጠባቂው የፍጻሜ ጨዋታ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 8፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ማንቼስተር ሲቲን ከቼልሲ የሚያገናኘው የእንግሊዝ ኤፍ ኤ ካፕ የፍጻሜ ጨዋታ ዛሬ አመሻሽ 11 ሰዓት ላይ በዌምብሌይ ስታዲየም ይደረጋል፡፡
በአሰልጣኝ ፔፕ ጋርዲዮላ የሚመራው ማንቼስተር ሲቲ በግማሽ ፍጻሜው ሳውዛምፕተንን 2 ለ 1 በማሸነፍ ለፍጻሜ መብቃቱ ይታወሳል፡፡
ማንቼስተር ሲቲ የዘንድሮውን ጨምሮ ያለፉትን አራት ተከታታይ ዓመታት በኤፍ ኤ ካፕ የፍጻሜ ጨዋታ ላይ መገኘት ችሏል፡፡
ሆኖም ካለፉት ሦስት የኤፍ ኤ ካፕ የፍጻሜ ጨዋታዎች ማሸነፍ የቻለው አንዱን ብቻ ሲሆን፥ ለመጨረሻ ጊዜ የዋንጫው ባለቤት የሆነው በፈረንጆቹ 2023 ነበር፡፡
ማንቼስተር ሲቲ በታሪኩ ሰባት ጊዜ የኤፍ ኤ ካፕ ዋንጫን ማሳካት የቻለ ሲሆን፥ ለስምንተኛ ጊዜ ሻምፒዮን ለመሆን የሚያደርገው ፍልሚያ ይጠበቃል፡፡
አስቀድሞ የካራባኦ ዋንጫን ያሳካው ሲቲ በዚህ የውድድር ዓመት 2ኛ ዋንጫውን ፍለጋ ወደ ሜዳ ይገባል፡፡
በውድድር ዓመቱ የሦስትዮሽ ዋንጫ የማሳካት እድል ያለው ማንቼስተር ሲቲ ጉዞውን አጠናክሮ ለመቀጠል ይፋለማል፡፡
እስካሁን አሸናፊው ባልተለየበት የሊጉ የዋንጫ ፉክክር ውስጥ የሚገኘው ማንቼስተር ሲቲ ይህንን ዋንጫ ማሳካት ከቻለ የሦስትዮሽ ዋንጫ ጉዞውን እንደሚያጠናክርለት ይታመናል፡፡
ተጋጣሚው ቼልሲ በበኩሉ በግማሽ ፍጻሜው ሊድስ ዩናይትድን በኢንዞ ፈርናንዴዝ ብቸኛ ግብ በመርታት ለፍጻሜ መድረሱ አይዘነጋም፡፡
በታሪኩ ስምንት ጊዜ የኤፍ ኤ ዋንጫን ማሳካት የቻለው የምዕራብ ለንደኑ ክለብ ቼልሲ ለ9ኛ ጊዜ በመድረኩ ሻምፒዮን ለመሆን ይፋለማል፡፡
አሰልጣኞች ቢለዋውጥም መሻሻል ያልቻለው ቼልሲ የውድድር ዓመቱን ያለምንም ዋንጫ ላለማጠናቀቅ ብርቱ ፉክክር ያደርጋል ተብሎ ይጠበቃል፡፡
የምዕራብ ለንደኑ ክለብ ለመጨረሻ ጊዜ የኤፍ ኤ ዋንጫን ማሳካት የቻለው በፈረንጆቹ 2018 እንደነበር ይታወሳል፡፡
ከዚያ ወዲህ ቼልሲ በ2021 እና በ2022 የፍጻሜ ተፋላሚ መሆን ቢችልም ዋንጫውን ግን ማሳካት አልቻለም፡፡
በ1871/72 በጀመረው የእንግሊዝ ኤፍ ኤ ዋንጫ ውድድር አርሰናል 14 ጊዜ የዋንጫው ባለቤት በመሆን ቀዳሚው ሲሆን፥ ማንቼስተር ዩናይትድ 13 ጊዜ በመድረኩ ሻምፒዮን በመሆን ይከተላል፡፡
የዛሬ የፍጻሜ ተፋላሚው ቼልሲ፣ ሊቨርፑል እና ቶተንሃም ሆትስፐር በተመሳሳይ ስምንት ጊዜ ሻምፒዮን ሆነዋል፡፡
ሌላኛው የምሽቱ የፍጻሜ ተፋላሚ ማንቼስተር ሲቲ እንዲሁም አስቶንቪላ በተመሳሳይ ሰባት ጊዜ የኤፍ ኤ ዋንጫን በማንሳት በርካታ ጊዜ ሻምፒዮን ከሆኑ ቡድኖች መካከል ይጠቀሳሉ፡፡
በዌምብሌይ ስታዲየም አመሻሽ 11 ሰዓት ላይ የሚደረገውን ተጠባቂ የፍጻሜ ጨዋታ እንግሊዛዊው ዳኛ ዳረን ኢንግላንድ በመሐል ዳኝነት የሚመሩት ይሆናል፡፡
በወንድማገኝ ጸጋዬ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 8፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ማንቼስተር ሲቲን ከቼልሲ የሚያገናኘው የእንግሊዝ ኤፍ ኤ ካፕ የፍጻሜ ጨዋታ ዛሬ አመሻሽ 11 ሰዓት ላይ በዌምብሌይ ስታዲየም ይደረጋል፡፡
በአሰልጣኝ ፔፕ ጋርዲዮላ የሚመራው ማንቼስተር ሲቲ በግማሽ ፍጻሜው ሳውዛምፕተንን 2 ለ 1 በማሸነፍ ለፍጻሜ መብቃቱ ይታወሳል፡፡
ማንቼስተር ሲቲ የዘንድሮውን ጨምሮ ያለፉትን አራት ተከታታይ ዓመታት በኤፍ ኤ ካፕ የፍጻሜ ጨዋታ ላይ መገኘት ችሏል፡፡
ሆኖም ካለፉት ሦስት የኤፍ ኤ ካፕ የፍጻሜ ጨዋታዎች ማሸነፍ የቻለው አንዱን ብቻ ሲሆን፥ ለመጨረሻ ጊዜ የዋንጫው ባለቤት የሆነው በፈረንጆቹ 2023 ነበር፡፡
ማንቼስተር ሲቲ በታሪኩ ሰባት ጊዜ የኤፍ ኤ ካፕ ዋንጫን ማሳካት የቻለ ሲሆን፥ ለስምንተኛ ጊዜ ሻምፒዮን ለመሆን የሚያደርገው ፍልሚያ ይጠበቃል፡፡
አስቀድሞ የካራባኦ ዋንጫን ያሳካው ሲቲ በዚህ የውድድር ዓመት 2ኛ ዋንጫውን ፍለጋ ወደ ሜዳ ይገባል፡፡
በውድድር ዓመቱ የሦስትዮሽ ዋንጫ የማሳካት እድል ያለው ማንቼስተር ሲቲ ጉዞውን አጠናክሮ ለመቀጠል ይፋለማል፡፡
እስካሁን አሸናፊው ባልተለየበት የሊጉ የዋንጫ ፉክክር ውስጥ የሚገኘው ማንቼስተር ሲቲ ይህንን ዋንጫ ማሳካት ከቻለ የሦስትዮሽ ዋንጫ ጉዞውን እንደሚያጠናክርለት ይታመናል፡፡
ተጋጣሚው ቼልሲ በበኩሉ በግማሽ ፍጻሜው ሊድስ ዩናይትድን በኢንዞ ፈርናንዴዝ ብቸኛ ግብ በመርታት ለፍጻሜ መድረሱ አይዘነጋም፡፡
በታሪኩ ስምንት ጊዜ የኤፍ ኤ ዋንጫን ማሳካት የቻለው የምዕራብ ለንደኑ ክለብ ቼልሲ ለ9ኛ ጊዜ በመድረኩ ሻምፒዮን ለመሆን ይፋለማል፡፡
አሰልጣኞች ቢለዋውጥም መሻሻል ያልቻለው ቼልሲ የውድድር ዓመቱን ያለምንም ዋንጫ ላለማጠናቀቅ ብርቱ ፉክክር ያደርጋል ተብሎ ይጠበቃል፡፡
የምዕራብ ለንደኑ ክለብ ለመጨረሻ ጊዜ የኤፍ ኤ ዋንጫን ማሳካት የቻለው በፈረንጆቹ 2018 እንደነበር ይታወሳል፡፡
ከዚያ ወዲህ ቼልሲ በ2021 እና በ2022 የፍጻሜ ተፋላሚ መሆን ቢችልም ዋንጫውን ግን ማሳካት አልቻለም፡፡
በ1871/72 በጀመረው የእንግሊዝ ኤፍ ኤ ዋንጫ ውድድር አርሰናል 14 ጊዜ የዋንጫው ባለቤት በመሆን ቀዳሚው ሲሆን፥ ማንቼስተር ዩናይትድ 13 ጊዜ በመድረኩ ሻምፒዮን በመሆን ይከተላል፡፡
የዛሬ የፍጻሜ ተፋላሚው ቼልሲ፣ ሊቨርፑል እና ቶተንሃም ሆትስፐር በተመሳሳይ ስምንት ጊዜ ሻምፒዮን ሆነዋል፡፡
ሌላኛው የምሽቱ የፍጻሜ ተፋላሚ ማንቼስተር ሲቲ እንዲሁም አስቶንቪላ በተመሳሳይ ሰባት ጊዜ የኤፍ ኤ ዋንጫን በማንሳት በርካታ ጊዜ ሻምፒዮን ከሆኑ ቡድኖች መካከል ይጠቀሳሉ፡፡
በዌምብሌይ ስታዲየም አመሻሽ 11 ሰዓት ላይ የሚደረገውን ተጠባቂ የፍጻሜ ጨዋታ እንግሊዛዊው ዳኛ ዳረን ኢንግላንድ በመሐል ዳኝነት የሚመሩት ይሆናል፡፡
በወንድማገኝ ጸጋዬ
3 months ago
አስቶን ቪላ ሊቨርፑልን በማሸነፍ የአውሮፖ ሻምፒዮንስ ሊግ ተሳትፎን አረጋገጠ
**************
በ37ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ አስቶን ቪላ ሊቨርፑልን 4 ለ 2 አሸንፏል።
በቪላ ፓርክ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ ኦሊ ዋትኪንስ ሁለት ግቦችን ለአስቶን ቪላ ማስቆጠር የቻለ ሲሆን፣ ሞርጋን ሮጀርስ እና ጆን ማክጊን ቀሪዎቹን ሁለት ግቦች አስቆጥረዋል።
ቨርጅል ቫን ዳይክ በጨዋታው ለሊቨርፑል ሁለቱንም ግቦች ማስቆጠር ችሏል።
በጨዋታው ወሳኝ ሦስት ነጥብ ያገኘው አስቶን ቪላ ነጥቡን 62 በማድረስ በቀጣይ አመት በአውሮፖ ሻምፒዮንስ ሊግ መሳተፉን አረጋግጧል።
በዘረንቶስ ሰለሞን
#ebc #premierleague #football
**************
በ37ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ አስቶን ቪላ ሊቨርፑልን 4 ለ 2 አሸንፏል።
በቪላ ፓርክ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ ኦሊ ዋትኪንስ ሁለት ግቦችን ለአስቶን ቪላ ማስቆጠር የቻለ ሲሆን፣ ሞርጋን ሮጀርስ እና ጆን ማክጊን ቀሪዎቹን ሁለት ግቦች አስቆጥረዋል።
ቨርጅል ቫን ዳይክ በጨዋታው ለሊቨርፑል ሁለቱንም ግቦች ማስቆጠር ችሏል።
በጨዋታው ወሳኝ ሦስት ነጥብ ያገኘው አስቶን ቪላ ነጥቡን 62 በማድረስ በቀጣይ አመት በአውሮፖ ሻምፒዮንስ ሊግ መሳተፉን አረጋግጧል።
በዘረንቶስ ሰለሞን
#ebc #premierleague #football
Sponsored by
Surafel
3 months ago
አስቶን ቪላ ሊቨርፑልን በማሸነፍ አራተኛ ደረጃ ላይ ተቀመጠ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 7፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ 37ኛ ሳምንት መርሐ ግብር አስቶን ቪላ ሊቨርፑልን 4 ለ 2 አሸንፏል።
ምሽት 4 ሰዓት ላይ በቪላ ፓርክ ስታዲየም ሊቨርፑልን ያስተናገደው አስቶን ቪላ ሮጀርስ፣ ዋትኪንስ (ሁለት) እና ማክጊን ባስቆጠሯቸው ግቦች ድል አድርጓል።
የሊቨርፑልን ግቦች ቫን ዳይክ ከመረብ አሳርፏል።
በዚህም አስቶን ቪላ ነጥቡን 62 በማድረስ አራተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል።
ሊጉን አርሰናል በ79 ነጥብ እየመራ ሲሆን÷ ማንቼስተር ሲቲ በ77 ነጥብ ሁለተኛ፣ ማንቼስተር ዩናይትድ በ65 ነጥብ ሶስተኛ ደረጃን ይዘዋል።
ሊቨርፑል በ59 ነጥብ አምስተኛ ደረጃ ላይ ይገኛል።
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 7፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ 37ኛ ሳምንት መርሐ ግብር አስቶን ቪላ ሊቨርፑልን 4 ለ 2 አሸንፏል።
ምሽት 4 ሰዓት ላይ በቪላ ፓርክ ስታዲየም ሊቨርፑልን ያስተናገደው አስቶን ቪላ ሮጀርስ፣ ዋትኪንስ (ሁለት) እና ማክጊን ባስቆጠሯቸው ግቦች ድል አድርጓል።
የሊቨርፑልን ግቦች ቫን ዳይክ ከመረብ አሳርፏል።
በዚህም አስቶን ቪላ ነጥቡን 62 በማድረስ አራተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል።
ሊጉን አርሰናል በ79 ነጥብ እየመራ ሲሆን÷ ማንቼስተር ሲቲ በ77 ነጥብ ሁለተኛ፣ ማንቼስተር ዩናይትድ በ65 ነጥብ ሶስተኛ ደረጃን ይዘዋል።
ሊቨርፑል በ59 ነጥብ አምስተኛ ደረጃ ላይ ይገኛል።
3 months ago
ለ3ኛ ተከታታይ የውድድር ዓመት የፈረንሳይ ሊግ ሻምፒዮን - አሰልጣኝ ሉዊስ ኤንሪኬ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 7፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ስፔናዊው አሰልጣኝ ሉዊስ ኤንሪኬ ለተከታታይ 3ኛ የውድድር ዓመት ከፒኤስጂ ጋር የፈረንሳይ ሊግ ዋንጫን ማሸነፍ ችለዋል፡፡
በፈረንጆቹ 1970 ስፔን ውስጥ በዛሬው ዕለት የተወለዱት አሰልጣኝ ሉዊስ ኤንሪኬ የአሰልጣኝነት ስራቸውን የጀመሩት በባርሴሎና ቢ ቡድን ነው፡፡
ከባርሴሎና ቢ ቡድን በመቀጠል ሮማ እና ሴልታቪጎን ያሰለጠኑት አሰልጣኙ በፈረንጆቹ 2014 የባርሴሎና ዋናውን ቡድን ተረክበዋል፡፡
በካታላኑ ክለብ ባርሴሎና በነበራቸው የአሰልጣኝነት ቆይታ የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ፣ የስፔን ላሊጋ፣ የስፔን ሱፐር ካፕ፣ ኮፓ ዴል ሬይ፣ የዓለም ክለቦች ዋንጫ እና የአውሮፓ ሱፐር ካፕ ዋንጫዎችን አሳክተዋል፡፡
ከባርሴሎና ጋር ከተለያዩ በኋላ የስፔን ብሔራዊ ቡድንን ከፈረንጆቹ 2018 እስከ 2022 አሰልጥነው በ2023/24 ወደ ፈረንሳዩ ክለብ ፒኤስጂ አቅንተዋል፡፡
የፓሪሱን ክለብ በ2023/24 ከተረከቡ ወዲህ የዘንድሮን ጨምሮ ለተከታታይ ሦስት የውድድር ዓመታት የሊጉን ዋንጫ ማሳካት ችለዋል፡፡
ፒኤስጂ በታሪኩ 14ኛ የፈረንሳይ ሊግ ዋንጫውን ያሳካ ሲሆን÷ በኤንሪኬ እየተመራ ደግሞ ያለፉትን ሦስት ተከታታይ የውድድር ዓመት ሻምፒዮን ሆኗል፡፡
ፒኤስጂ በሀገር ውስጥ ውድድር ስኬታማ ቢሆንም በአውሮፓ መድረክ ግን ተፎካካሪ ለመሆን እና ዋንጫ ለማንሳት የኤንሪኬን ፓሪስ መድረስ ይፈልግ ነበር፡፡
ፒኤስጂ የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ዋንጫን ለማሳካት ሊዮኔል ሜሲ፣ ኔይማር ጁኒየር እና ኪሊያን ምባፔ የመሳሳሉ ተጫዋቾችን ቢያጣምርም ማሳካት እንዳልቻለ ይታወቃል፡፡
ከስፔናዊው አሰልጣኝ ሉዊስ ኤንሪኬ ፓሪስ መድረስ በኋላ ግን የክለቡ የዘመናት ጥያቄ ባሳለፍነው የውድድር ዘመን ምላሽ ማግኘቱ ይታወሳል፡፡
አሰልጣኝ ሉዊስ ኤንሪኬ የፈረንሳዩን ክለብ የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ የዘመናት ሕልም መፍታት የቻሉ ሰው ናቸው፡፡
ፒኤስጂ በታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ዋንጫን በፈረንጆቹ 2024/25 የውድድር ዓመት ሲያሳካ አሰልጣኝ ሉዊስ ኤንሪኬ በክለቡ ያመጡት ለውጥ ቀላል የሚባል አይደለም፡፡
አሰልጣኙ በአንድ ተጫዋች ላይ ጥገኛ ያልሆነ እንደ ቡድን የሚጫወት ጠንካራ ስብስብ በመገንባት ክለቡን ለዚህ ታላቅ ክብር አብቅተዋል፡፡
አሰልጣኝ ሉዊስ ኤንሪኬ አሁን የፈረንሳዩን ክለብ ፒኤስጂን በአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ መድረክ ለተከታታይ የውድድር ዓመት ለፍጻሜ ማድረስ ችለዋል፡፡
የአሰልጣኝ ኤንሪኬ ቡድን በዚህ የውድድር ዓመት በአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ተጋጣሚዎቹ ላይ 44 ግቦችን ያስቆጠረ ሲሆን÷ በዚህም በውድድር ዘመኑ በመድረኩ በርካታ ግቦችን በማስቆጠር ቀዳሚው ሆኗል።
ቡድኑ በዚህ የውድድር ዓመት በመድረኩ ባየርን ሙኒክ፣ ሊቨርፑል፣ ቼልሲ እና ባርሴሎናን የመሳሰሉ ቡድኖችን ማሸነፉ ይታወሳል፡፡
ፒኤስጂ በአሰልጣኝ ሉዊስ ኤንሪኬ እየተመራ ለተከታታይ የውድድር ዓመት የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ዋንጫን ያሳካ ይሆን የሚለው የሚጠበቅ ሲሆን÷ በፍጻሜው ከአርሰናል ጋር ጨዋታውን ያደርጋል፡፡
የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ የፍጻሜ ጨዋታ ግንቦት 22 ቀን 2018 ዓ.ም በሀንጋሪ ቡዳፔስት ፑሽካሽ አሬና ስታዲየም ይደረጋል።
በወንድማገኝ ጸጋዬ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 7፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ስፔናዊው አሰልጣኝ ሉዊስ ኤንሪኬ ለተከታታይ 3ኛ የውድድር ዓመት ከፒኤስጂ ጋር የፈረንሳይ ሊግ ዋንጫን ማሸነፍ ችለዋል፡፡
በፈረንጆቹ 1970 ስፔን ውስጥ በዛሬው ዕለት የተወለዱት አሰልጣኝ ሉዊስ ኤንሪኬ የአሰልጣኝነት ስራቸውን የጀመሩት በባርሴሎና ቢ ቡድን ነው፡፡
ከባርሴሎና ቢ ቡድን በመቀጠል ሮማ እና ሴልታቪጎን ያሰለጠኑት አሰልጣኙ በፈረንጆቹ 2014 የባርሴሎና ዋናውን ቡድን ተረክበዋል፡፡
በካታላኑ ክለብ ባርሴሎና በነበራቸው የአሰልጣኝነት ቆይታ የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ፣ የስፔን ላሊጋ፣ የስፔን ሱፐር ካፕ፣ ኮፓ ዴል ሬይ፣ የዓለም ክለቦች ዋንጫ እና የአውሮፓ ሱፐር ካፕ ዋንጫዎችን አሳክተዋል፡፡
ከባርሴሎና ጋር ከተለያዩ በኋላ የስፔን ብሔራዊ ቡድንን ከፈረንጆቹ 2018 እስከ 2022 አሰልጥነው በ2023/24 ወደ ፈረንሳዩ ክለብ ፒኤስጂ አቅንተዋል፡፡
የፓሪሱን ክለብ በ2023/24 ከተረከቡ ወዲህ የዘንድሮን ጨምሮ ለተከታታይ ሦስት የውድድር ዓመታት የሊጉን ዋንጫ ማሳካት ችለዋል፡፡
ፒኤስጂ በታሪኩ 14ኛ የፈረንሳይ ሊግ ዋንጫውን ያሳካ ሲሆን÷ በኤንሪኬ እየተመራ ደግሞ ያለፉትን ሦስት ተከታታይ የውድድር ዓመት ሻምፒዮን ሆኗል፡፡
ፒኤስጂ በሀገር ውስጥ ውድድር ስኬታማ ቢሆንም በአውሮፓ መድረክ ግን ተፎካካሪ ለመሆን እና ዋንጫ ለማንሳት የኤንሪኬን ፓሪስ መድረስ ይፈልግ ነበር፡፡
ፒኤስጂ የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ዋንጫን ለማሳካት ሊዮኔል ሜሲ፣ ኔይማር ጁኒየር እና ኪሊያን ምባፔ የመሳሳሉ ተጫዋቾችን ቢያጣምርም ማሳካት እንዳልቻለ ይታወቃል፡፡
ከስፔናዊው አሰልጣኝ ሉዊስ ኤንሪኬ ፓሪስ መድረስ በኋላ ግን የክለቡ የዘመናት ጥያቄ ባሳለፍነው የውድድር ዘመን ምላሽ ማግኘቱ ይታወሳል፡፡
አሰልጣኝ ሉዊስ ኤንሪኬ የፈረንሳዩን ክለብ የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ የዘመናት ሕልም መፍታት የቻሉ ሰው ናቸው፡፡
ፒኤስጂ በታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ዋንጫን በፈረንጆቹ 2024/25 የውድድር ዓመት ሲያሳካ አሰልጣኝ ሉዊስ ኤንሪኬ በክለቡ ያመጡት ለውጥ ቀላል የሚባል አይደለም፡፡
አሰልጣኙ በአንድ ተጫዋች ላይ ጥገኛ ያልሆነ እንደ ቡድን የሚጫወት ጠንካራ ስብስብ በመገንባት ክለቡን ለዚህ ታላቅ ክብር አብቅተዋል፡፡
አሰልጣኝ ሉዊስ ኤንሪኬ አሁን የፈረንሳዩን ክለብ ፒኤስጂን በአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ መድረክ ለተከታታይ የውድድር ዓመት ለፍጻሜ ማድረስ ችለዋል፡፡
የአሰልጣኝ ኤንሪኬ ቡድን በዚህ የውድድር ዓመት በአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ተጋጣሚዎቹ ላይ 44 ግቦችን ያስቆጠረ ሲሆን÷ በዚህም በውድድር ዘመኑ በመድረኩ በርካታ ግቦችን በማስቆጠር ቀዳሚው ሆኗል።
ቡድኑ በዚህ የውድድር ዓመት በመድረኩ ባየርን ሙኒክ፣ ሊቨርፑል፣ ቼልሲ እና ባርሴሎናን የመሳሰሉ ቡድኖችን ማሸነፉ ይታወሳል፡፡
ፒኤስጂ በአሰልጣኝ ሉዊስ ኤንሪኬ እየተመራ ለተከታታይ የውድድር ዓመት የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ዋንጫን ያሳካ ይሆን የሚለው የሚጠበቅ ሲሆን÷ በፍጻሜው ከአርሰናል ጋር ጨዋታውን ያደርጋል፡፡
የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ የፍጻሜ ጨዋታ ግንቦት 22 ቀን 2018 ዓ.ም በሀንጋሪ ቡዳፔስት ፑሽካሽ አሬና ስታዲየም ይደረጋል።
በወንድማገኝ ጸጋዬ
3 months ago
ማንቼስተር ሲቲ ከአርሰናል ጋር ያለውን የነጥብ ልዩነት አጠበበ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 5፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ተስተካካይ ጨዋታ ማንቼስተር ሲቲ ክሪስታል ፓላስን 3 ለ 0 አሸንፏል።
በዚህም ከሊጉ መሪ አርሰናል ጋር ያለውን የነጥብ ልዩነት ወደ ሁለት አጥብቧል።
ምሽት 4 ሰዓት ላይ በኢቲሃድ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ማንቼስተር ሲቲ ሴሜንዮ፣ ማርሙሽ እና ሳቪኒሆ ባስቆጠሯቸው ግቦች ክሪስታል ፓላስን በማሸነፍ የዋንጫ ፉክክር ውስጥ መቆየት ችሏል።
ሊጉን አርሰናል በ79 ነጥብ እየመራ ሲሆን÷ ማንቼስተር ሲቲ በ77 ነጥብ፣ ማንቼስተር ዩናይትድ በ65 እንዲሁም ሊቨርፑል በ59 ነጥብ ከ2ኛ እስከ 4ኛ ያለውን ደረጃ ይዘዋል።
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 5፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ተስተካካይ ጨዋታ ማንቼስተር ሲቲ ክሪስታል ፓላስን 3 ለ 0 አሸንፏል።
በዚህም ከሊጉ መሪ አርሰናል ጋር ያለውን የነጥብ ልዩነት ወደ ሁለት አጥብቧል።
ምሽት 4 ሰዓት ላይ በኢቲሃድ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ማንቼስተር ሲቲ ሴሜንዮ፣ ማርሙሽ እና ሳቪኒሆ ባስቆጠሯቸው ግቦች ክሪስታል ፓላስን በማሸነፍ የዋንጫ ፉክክር ውስጥ መቆየት ችሏል።
ሊጉን አርሰናል በ79 ነጥብ እየመራ ሲሆን÷ ማንቼስተር ሲቲ በ77 ነጥብ፣ ማንቼስተር ዩናይትድ በ65 እንዲሁም ሊቨርፑል በ59 ነጥብ ከ2ኛ እስከ 4ኛ ያለውን ደረጃ ይዘዋል።
3 months ago
ማንቼስተር ሲቲን በዋንጫ ፉክክር ውስጥ የሚያቆየው ወሳኝ ጨዋታ…
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 5፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ተስተካካይ ጨዋታ ማንቼስተር ሲቲ በኢቲሃድ ስታዲየም ከክሪስታል ፓላስ ጋር የሚያደርገው ፍልሚያ ይጠበቃል፡፡
ምሽት አራት ሰዓት ላይ በሚካሄደው በዚህ ጨዋታ ማንቼስተር ሲቲ በሊጉ የዋንጫ ፉክክር ውስጥ ለመቆየት ግጥሚያውን ማሸነፍ ይጠበቅበታል፡፡
ሲቲ የምሽቱን ጨዋታ ከተሸነፈ ወይም አቻ ከወጣ እንዲሁም አርሰናል በመጪው ሰኞ ከሊጉ መውረዱን ካረጋገጠው በርንሌይ የሚያደርገውን ጨዋታ ማሸነፍ ከቻለ የ2025/26 የውድድር ዘመን ሻምፒዮን መሆኑን ያረጋግጣል፡፡
አንድ ቀሪ ጨዋታ እያለው ከመሪው አርሰናል በአምስት ነጥብ አንሶ ሁለተኛ ደረጃ ላይ የሚገኘው ማንቼስተር ሲቲ÷ የምሽቱን ጨዋታ ካሸነፈ ልዩነቱን ወደ ሁለት በማጠበብ በሊጉ የዋንጫ ፉክክር ውስጥ የሚቆይ ይሆናል፡፡
ሊጉን አርሰናል በ79 ነጥብ እየመራ ሲሆን÷ ማንቼስተር ሲቲ በ74 ነጥብ፣ ማንቼስተር ዩናይትድ በ65 እንዲሁም ሊቨርፑል በ59 ነጥብ ከ2ኛ አስከ 4ኛ ደረጃ በመያዝ ይከተላሉ።
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 5፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ተስተካካይ ጨዋታ ማንቼስተር ሲቲ በኢቲሃድ ስታዲየም ከክሪስታል ፓላስ ጋር የሚያደርገው ፍልሚያ ይጠበቃል፡፡
ምሽት አራት ሰዓት ላይ በሚካሄደው በዚህ ጨዋታ ማንቼስተር ሲቲ በሊጉ የዋንጫ ፉክክር ውስጥ ለመቆየት ግጥሚያውን ማሸነፍ ይጠበቅበታል፡፡
ሲቲ የምሽቱን ጨዋታ ከተሸነፈ ወይም አቻ ከወጣ እንዲሁም አርሰናል በመጪው ሰኞ ከሊጉ መውረዱን ካረጋገጠው በርንሌይ የሚያደርገውን ጨዋታ ማሸነፍ ከቻለ የ2025/26 የውድድር ዘመን ሻምፒዮን መሆኑን ያረጋግጣል፡፡
አንድ ቀሪ ጨዋታ እያለው ከመሪው አርሰናል በአምስት ነጥብ አንሶ ሁለተኛ ደረጃ ላይ የሚገኘው ማንቼስተር ሲቲ÷ የምሽቱን ጨዋታ ካሸነፈ ልዩነቱን ወደ ሁለት በማጠበብ በሊጉ የዋንጫ ፉክክር ውስጥ የሚቆይ ይሆናል፡፡
ሊጉን አርሰናል በ79 ነጥብ እየመራ ሲሆን÷ ማንቼስተር ሲቲ በ74 ነጥብ፣ ማንቼስተር ዩናይትድ በ65 እንዲሁም ሊቨርፑል በ59 ነጥብ ከ2ኛ አስከ 4ኛ ደረጃ በመያዝ ይከተላሉ።
Sponsored by
Surafel
3 months ago
(ዘ-ሐበሻ ስፖርት) የፕሪሚየር ሊጉ የዋንጫ ፉክክር ወደ መጨረሻው እና ወሳኙ ምዕራፍ በተሸጋገረበት በዚህ ወቅት፣ ማንችስተር ሲቲ ማሸነፍ ግድ ይለው በነበረው ጨዋታ ብሬንትፎርድን በማንበርከክ የዋንጫ ተስፋውን አለምልሟል። ሰኞ እለት ከኤቨርተን ጋር 3 ለ 3 ተለያይተው ውድ ነጥብ ጥለው የነበሩት የፔፕ ጋርዲዮላ ልጆች፣ በሁለተኛው አጋማሽ ባስቆጠሯቸው ሶስት ግቦች የሊጉን መሪ አርሰናልን የነጥብ ልዩነት ወደ ሁለት ዝቅ ማድረግ ችለዋል። አሁን የሲቲ አይን ያረፈው፣ ሚካኤል አርቴታ የሚመራው አርሰናል እሁድ እለት ከመውረድ ስጋት ውስጥ ከሚገኘው ዌስትሃም ጋር በሚያደርገው ወሳኝ ጨዋታ ላይ ነው።
በሜዳው ላይ ልዩነት ፈጣሪ የነበረው ቤልጄሚያዊው ኮከብ ጀረሚ ዶኩ ነው። ገና በሁለተኛው ደቂቃ የብሬንትፎርዱን ግብ ጠባቂ ኩዊቪን ኬለኸርን የፈተነ ሙከራ ያደረገው ዶኩ፣ ብዙም ሳይቆይ ኤርሊንግ ሀላንድ በግንባር ገጭቶ ለሳተው ኳስም አመቻችቶ አቀብሎ ነበር። በመጀመሪያው አጋማሽ ሲቲዎች በርካታ ሙከራዎችን ቢያደርጉም ግብ ማስቆጠር ተስኗቸው በብስጭት ወደ መልበሻ ቤት አምርተዋል። ሀላንድ በቀጥታ በኬለኸር ላይ የሞከረው እና ክሪስቶፈር አየር ያዳነበት ኳስ የዚሁ ብስጭት ማሳያዎች ነበሩ።
ነገር ግን በ60ኛው ደቂቃ ላይ ያቺ የተጠበቀችው ወሳኝ ግብ ተቆጠረች። ጀረሚ ዶኩ ኳስን ወደ ውስጥ ይዞ በመግባት እጅግ ማራኪ በሆነ አጨራረስ የብሬንትፎርድን መረብ አናወጠ፤ ልክ ሰኞ እለት በኤቨርተን ላይ ቡድኑን ከሽንፈት በታደገበት አኳኋን! ከ15 ደቂቃዎች በኋላ (በ75ኛው ደቂቃ) ደግሞ ኤርሊንግ ሀላንድ በግፊያ ውስጥ ሁለተኛዋን ግብ በማስቆጠር የኢትሀድ ስታዲየምን ድባብ አቀለጠው። በጭማሪ ሰዓት (92ኛው ደቂቃ) ተቀይሮ የገባው ኦማር ማርሙሽ የሲቲን ሶስተኛ ግብ አክሎ የድሉን ሪቫን በቆረጠበት ሰዓት፣ ባለሜዳዎቹ ሙሉ ሶስት ነጥብ ማረጋገጥ ችለዋል።
ውጤቱ 3-0 ይሁን እንጂ እንግዳው ብሬንትፎርድ ቀላል ተጋጣሚ አልነበረም። የሲቲው ግብ ጠባቂ ጂያንሉዊጂ ዶናሩማ የጣሊያን ብሄራዊ ቡድን አምበልነቱን በሚመጥን ብቃት ቡድኑን ታድጓል። ማይክል ካዮዴ በረጅሙ የወረወረውን፣ ማቲያስ ጀንሰን ያሻማውን አደገኛ የቅጣት ምት፣ እንዲሁም ኢጎር ቲያጎ በሁለተኛው አጋማሽ በቅርብ ርቀት የሞከረውን ኳስ ዶናሩማ በሚገርም ቅልጥፍና አድኖታል። በዚህም ሲቲ መረቡን ሳያስደፍር ሲወጣ፣ ብሬንትፎርድ በሊጉ 8ኛ ደረጃ ላይ እንዲረጋ ሆኗል።
በእረፍት ሰዓት የሲቲ ደጋፊዎች በቡድኑ እንቅስቃሴ ቅሬታቸውን ሲያሰሙ ነበር። ነገር ግን ጋርዲዮላ ተጫዋቾቹን አነቃቅቶ በሁለተኛው አጋማሽ ባስቆጠሯቸው ግቦች አጓጊውን የዋንጫ ፉክክር ዳግም አሙቀውታል። አሁን ሲቲዎች ዋንጫውን ለማንሳት የአርሰናልን ነጥብ መጣል የሚጠብቁ ሲሆን፣ በቀጣይ ከክሪስታል ፓላስ እና በርንማውዝ ጋር የሚያደርጉትን ጨዋታ ማሸነፍ ግድ ይላቸዋል።
ይህ ድል ሲቲ በሜዳው ያለመሸነፍ ክብረ ወሰኑን ወደ 16 ጨዋታዎች ከፍ እንዲል አድርጎለታል (በነሐሴ ወር ከስፐርስ ከደረሰበት ሽንፈት ውጪ)። የሲቲ የግብ ልዩነት አሁን +40 የደረሰ ሲሆን፣ ከአርሰናል (+41) በአንድ ግብ ብቻ ዝቅ ብሏል። ተቀይሮ የገባው ፊል ፎደን ያደረገው ሙከራ በኬለኸር ባይድን ኖሮ የግብ ልዩነታቸውን እኩል ማድረግ በቻሉ ነበር። ይሁን እንጂ ዋናው ነገር ሶስቱ ነጥብ ነው።
አሰልጣኝ ኪዝ አንድሪውስ በመጀመሪያው የውድድር ዘመናቸው ጥሩ ስራ ቢሰሩም፣ አሁን ግን ቡድናቸው ከመጨረሻዎቹ 8 ጨዋታዎች ያሸነፈው አንዱን ብቻ ነው። በሊጉ 22 ግቦችን በማስቆጠር ሁለተኛ ደረጃ ላይ የሚገኘው አጥቂው ኢጎር ቲያጎም በዚህ ጨዋታ ላይ ከሀላንድ የተሻለ ተጽዕኖ መፍጠር አልቻለም።
ብሬንትፎርዶች በዕለቱ ዳኛ ማይክል ሳሊስበሪ ውሳኔዎች በእጅጉ ተበሳጭተዋል። በተለይም የሲቲው አምበል ቤርናርዶ ሲልቫ በመጀመሪያው አጋማሽ ናታን ኮሊንስ ላይ ላሳየው ጥቃት በቢጫ ካርድ ብቻ መታለፉ፣ እንዲሁም ማቲየስ ኑኔዝ በኬቪን ሻዴ ላይ የሰራቸው ሊሆኑ የሚችሉ ሁለት ጥፋቶች በቫር (VAR) ታይተው ምንም ሳይባል ማለፉ እንግዶቹን አስቆጥቷል። አሁን ብሬንትፎርድ ክሪስታል ፓላስን እና ሊቨርፑልን በሚገጥምባቸው ቀሪ ሁለት ጨዋታዎች ወደ አሸናፊነት በመመለስ የአውሮፓ ተሳትፎ ተስፋውን ለማለምለም እና ውድድር ዘመኑን በውበት ለማጠናቀቅ ይጥራል።
በሜዳው ላይ ልዩነት ፈጣሪ የነበረው ቤልጄሚያዊው ኮከብ ጀረሚ ዶኩ ነው። ገና በሁለተኛው ደቂቃ የብሬንትፎርዱን ግብ ጠባቂ ኩዊቪን ኬለኸርን የፈተነ ሙከራ ያደረገው ዶኩ፣ ብዙም ሳይቆይ ኤርሊንግ ሀላንድ በግንባር ገጭቶ ለሳተው ኳስም አመቻችቶ አቀብሎ ነበር። በመጀመሪያው አጋማሽ ሲቲዎች በርካታ ሙከራዎችን ቢያደርጉም ግብ ማስቆጠር ተስኗቸው በብስጭት ወደ መልበሻ ቤት አምርተዋል። ሀላንድ በቀጥታ በኬለኸር ላይ የሞከረው እና ክሪስቶፈር አየር ያዳነበት ኳስ የዚሁ ብስጭት ማሳያዎች ነበሩ።
ነገር ግን በ60ኛው ደቂቃ ላይ ያቺ የተጠበቀችው ወሳኝ ግብ ተቆጠረች። ጀረሚ ዶኩ ኳስን ወደ ውስጥ ይዞ በመግባት እጅግ ማራኪ በሆነ አጨራረስ የብሬንትፎርድን መረብ አናወጠ፤ ልክ ሰኞ እለት በኤቨርተን ላይ ቡድኑን ከሽንፈት በታደገበት አኳኋን! ከ15 ደቂቃዎች በኋላ (በ75ኛው ደቂቃ) ደግሞ ኤርሊንግ ሀላንድ በግፊያ ውስጥ ሁለተኛዋን ግብ በማስቆጠር የኢትሀድ ስታዲየምን ድባብ አቀለጠው። በጭማሪ ሰዓት (92ኛው ደቂቃ) ተቀይሮ የገባው ኦማር ማርሙሽ የሲቲን ሶስተኛ ግብ አክሎ የድሉን ሪቫን በቆረጠበት ሰዓት፣ ባለሜዳዎቹ ሙሉ ሶስት ነጥብ ማረጋገጥ ችለዋል።
ውጤቱ 3-0 ይሁን እንጂ እንግዳው ብሬንትፎርድ ቀላል ተጋጣሚ አልነበረም። የሲቲው ግብ ጠባቂ ጂያንሉዊጂ ዶናሩማ የጣሊያን ብሄራዊ ቡድን አምበልነቱን በሚመጥን ብቃት ቡድኑን ታድጓል። ማይክል ካዮዴ በረጅሙ የወረወረውን፣ ማቲያስ ጀንሰን ያሻማውን አደገኛ የቅጣት ምት፣ እንዲሁም ኢጎር ቲያጎ በሁለተኛው አጋማሽ በቅርብ ርቀት የሞከረውን ኳስ ዶናሩማ በሚገርም ቅልጥፍና አድኖታል። በዚህም ሲቲ መረቡን ሳያስደፍር ሲወጣ፣ ብሬንትፎርድ በሊጉ 8ኛ ደረጃ ላይ እንዲረጋ ሆኗል።
በእረፍት ሰዓት የሲቲ ደጋፊዎች በቡድኑ እንቅስቃሴ ቅሬታቸውን ሲያሰሙ ነበር። ነገር ግን ጋርዲዮላ ተጫዋቾቹን አነቃቅቶ በሁለተኛው አጋማሽ ባስቆጠሯቸው ግቦች አጓጊውን የዋንጫ ፉክክር ዳግም አሙቀውታል። አሁን ሲቲዎች ዋንጫውን ለማንሳት የአርሰናልን ነጥብ መጣል የሚጠብቁ ሲሆን፣ በቀጣይ ከክሪስታል ፓላስ እና በርንማውዝ ጋር የሚያደርጉትን ጨዋታ ማሸነፍ ግድ ይላቸዋል።
ይህ ድል ሲቲ በሜዳው ያለመሸነፍ ክብረ ወሰኑን ወደ 16 ጨዋታዎች ከፍ እንዲል አድርጎለታል (በነሐሴ ወር ከስፐርስ ከደረሰበት ሽንፈት ውጪ)። የሲቲ የግብ ልዩነት አሁን +40 የደረሰ ሲሆን፣ ከአርሰናል (+41) በአንድ ግብ ብቻ ዝቅ ብሏል። ተቀይሮ የገባው ፊል ፎደን ያደረገው ሙከራ በኬለኸር ባይድን ኖሮ የግብ ልዩነታቸውን እኩል ማድረግ በቻሉ ነበር። ይሁን እንጂ ዋናው ነገር ሶስቱ ነጥብ ነው።
አሰልጣኝ ኪዝ አንድሪውስ በመጀመሪያው የውድድር ዘመናቸው ጥሩ ስራ ቢሰሩም፣ አሁን ግን ቡድናቸው ከመጨረሻዎቹ 8 ጨዋታዎች ያሸነፈው አንዱን ብቻ ነው። በሊጉ 22 ግቦችን በማስቆጠር ሁለተኛ ደረጃ ላይ የሚገኘው አጥቂው ኢጎር ቲያጎም በዚህ ጨዋታ ላይ ከሀላንድ የተሻለ ተጽዕኖ መፍጠር አልቻለም።
ብሬንትፎርዶች በዕለቱ ዳኛ ማይክል ሳሊስበሪ ውሳኔዎች በእጅጉ ተበሳጭተዋል። በተለይም የሲቲው አምበል ቤርናርዶ ሲልቫ በመጀመሪያው አጋማሽ ናታን ኮሊንስ ላይ ላሳየው ጥቃት በቢጫ ካርድ ብቻ መታለፉ፣ እንዲሁም ማቲየስ ኑኔዝ በኬቪን ሻዴ ላይ የሰራቸው ሊሆኑ የሚችሉ ሁለት ጥፋቶች በቫር (VAR) ታይተው ምንም ሳይባል ማለፉ እንግዶቹን አስቆጥቷል። አሁን ብሬንትፎርድ ክሪስታል ፓላስን እና ሊቨርፑልን በሚገጥምባቸው ቀሪ ሁለት ጨዋታዎች ወደ አሸናፊነት በመመለስ የአውሮፓ ተሳትፎ ተስፋውን ለማለምለም እና ውድድር ዘመኑን በውበት ለማጠናቀቅ ይጥራል።
3 months ago
ማንቸስተር ሲቲ ብሬንትፎርድን በመርታት የዋንጫ ተፎካካሪነቱን አጠናከረ
#ethiopia | በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የ36ኛ ሳምንት መርሃ ግብር ማንቸስተር ሲቲ በገዛ ሜዳው ኢቲሃድ ስታዲየም ብሬንትፎርድን አስተናግዶ 3 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸንፏል።
ጨዋታው እስከ 60ኛው ደቂቃ ድረስ ያለምንም ግብ ቢቀጥልም በሁለተኛው አጋማሽ የሲቲ አጥቂዎች ባሳዩት ድንቅ ብቃት ድል ቀንቷቸዋል።
ለውሃ ሰማያዊዎቹ ግቦቹን ጄረሚ ዶኩ፣ አርሊንግ ሃላንድ እና ኦማር ማርሙሽ ከመረብ አሳርፈዋል።
ይህንን ውጤት ተከትሎ ማንቸስተር ሲቲ በሊጉ 22ኛ ድሉን በማስመዝገብ ነጥቡን ወደ 74 ከፍ አድርጓል።
ይህም ከመሪው አርሰናል ጋር ያለውን የነጥብ ልዩነት ወደ ሁለት ብቻ ዝቅ እንዲል አድርጎታል።
ኖርዌያዊው የግብ ማሽን አርሊንግ ሃላንድ በሊጉ ያስቆጠራቸውን ጎሎች ብዛት 25 በማድረስ ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነቱን በበላይነት እየመራ ይገኛል።
በሌላ በኩል በሊጉ መሪነት ላይ የሚገኘው አርሰናል ነገ ከዌስትሃም ዩናይትድ ጋር የሚያደርገው ጨዋታ በዋንጫ ፉክክሩ ላይ ትልቅ ተጽዕኖ ይኖረዋል ተብሎ ይጠበቃል።
ብሬንትፎርድ በበኩሉ በዚህ የውድድር ዓመት የ13ኛ ሽንፈቱን ያስተናገደ ሲሆን በ51 ነጥብ 8ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል።
በተያያዘ ዜና ማንቸስተር ዩናይትድ እና ሊቨርፑል በሳምንቱ መርሃ ግብራቸው ነጥብ መጋራታቸው ታውቋል።
#manchestercity #premierleague #footballnews #mancity #haaland #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የ36ኛ ሳምንት መርሃ ግብር ማንቸስተር ሲቲ በገዛ ሜዳው ኢቲሃድ ስታዲየም ብሬንትፎርድን አስተናግዶ 3 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸንፏል።
ጨዋታው እስከ 60ኛው ደቂቃ ድረስ ያለምንም ግብ ቢቀጥልም በሁለተኛው አጋማሽ የሲቲ አጥቂዎች ባሳዩት ድንቅ ብቃት ድል ቀንቷቸዋል።
ለውሃ ሰማያዊዎቹ ግቦቹን ጄረሚ ዶኩ፣ አርሊንግ ሃላንድ እና ኦማር ማርሙሽ ከመረብ አሳርፈዋል።
ይህንን ውጤት ተከትሎ ማንቸስተር ሲቲ በሊጉ 22ኛ ድሉን በማስመዝገብ ነጥቡን ወደ 74 ከፍ አድርጓል።
ይህም ከመሪው አርሰናል ጋር ያለውን የነጥብ ልዩነት ወደ ሁለት ብቻ ዝቅ እንዲል አድርጎታል።
ኖርዌያዊው የግብ ማሽን አርሊንግ ሃላንድ በሊጉ ያስቆጠራቸውን ጎሎች ብዛት 25 በማድረስ ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነቱን በበላይነት እየመራ ይገኛል።
በሌላ በኩል በሊጉ መሪነት ላይ የሚገኘው አርሰናል ነገ ከዌስትሃም ዩናይትድ ጋር የሚያደርገው ጨዋታ በዋንጫ ፉክክሩ ላይ ትልቅ ተጽዕኖ ይኖረዋል ተብሎ ይጠበቃል።
ብሬንትፎርድ በበኩሉ በዚህ የውድድር ዓመት የ13ኛ ሽንፈቱን ያስተናገደ ሲሆን በ51 ነጥብ 8ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል።
በተያያዘ ዜና ማንቸስተር ዩናይትድ እና ሊቨርፑል በሳምንቱ መርሃ ግብራቸው ነጥብ መጋራታቸው ታውቋል።
#manchestercity #premierleague #footballnews #mancity #haaland #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
3 months ago
ማንቼስተር ሲቲ ብሬንትፎርድን አሸነፈ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 1፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የ36ኛ ሳምንት መርሐግብር ማንቼስተር ሲቲ ብሬንትፎርድን 3 ለ 0 አሸንፏል፡፡
ምሽት 1 ሰዓት ከ30 በኢትሃድ በተደረገው ጨዋታ የውሃ ሰማያዊዎቹን ግቦች ዶኩ፣ ሀላንድ እና ማርሙሽ በ2ኛው አጋማሽ ከመረብ አሳርፈዋል፡፡
ውጤቱን ተከትሎ ማንቼስተር ሲቲ ነጥቡን 74 በማድረስ ከመሪው አርሰናል ጋር ያለውን የነጥብ ልዩነት ወደ ሁለት ማጥበብ ችሏል፡፡
ቀደም ሲል በተደረጉ የሊጉ ጨዋታዎች ማንቼስተር ዩናይትድ ከሰንድርላንድ 0 ለ 0፣ ሊቨርፑል ከቼልሲ 1 ለ 1 አቻ ሲለያዩ፥ ብራይተን ወልቭስን 3 ለ 0 እንዲሁም በርንማውዝ ፉልሃምን 1 ለ 0 አሸንፈዋል፡፡
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 1፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የ36ኛ ሳምንት መርሐግብር ማንቼስተር ሲቲ ብሬንትፎርድን 3 ለ 0 አሸንፏል፡፡
ምሽት 1 ሰዓት ከ30 በኢትሃድ በተደረገው ጨዋታ የውሃ ሰማያዊዎቹን ግቦች ዶኩ፣ ሀላንድ እና ማርሙሽ በ2ኛው አጋማሽ ከመረብ አሳርፈዋል፡፡
ውጤቱን ተከትሎ ማንቼስተር ሲቲ ነጥቡን 74 በማድረስ ከመሪው አርሰናል ጋር ያለውን የነጥብ ልዩነት ወደ ሁለት ማጥበብ ችሏል፡፡
ቀደም ሲል በተደረጉ የሊጉ ጨዋታዎች ማንቼስተር ዩናይትድ ከሰንድርላንድ 0 ለ 0፣ ሊቨርፑል ከቼልሲ 1 ለ 1 አቻ ሲለያዩ፥ ብራይተን ወልቭስን 3 ለ 0 እንዲሁም በርንማውዝ ፉልሃምን 1 ለ 0 አሸንፈዋል፡፡
3 months ago
ማንቼስተር ዩናይትድ ከሰንደርላንድ 0 - 0
ቦርንማውዝ ፉልሃምን 1 ለ 0
ብራይተን ወልቭስን 3 ለ 0
#ethiopia | በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የ36ኛ ሳምንት መርሃ ግብር ማንቼስተር ዩናይትድ ከሜዳው ውጭ ከሰንደርላንድ ጋር ያደረገው ጨዋታ ያለ ምንም ግብ በአቻ ውጤት ተጠናቋል።
ቀይ ሰይጣኖቹ ከሦስት ተከታታይ ድሎች በኋላ ነጥብ ለመጀመሪያ ጊዜ የተጋሩበት አጋጣሚ ሆኖ ተመዝግቧል።
በሌላ በኩል ቦርንማውዝ ፉልሃምን 1 ለ 0 በሆነ ውጤት በማሸነፍ በአውሮፓ መድረክ የመሳተፍ ተስፋውን አድሷል።
በዚህ ጨዋታ ከሁለቱም ወገን አንደርሰን እና ክሪስት በፈጸሙት ጥፋት በቀይ ካርድ ከሜዳ ተሰናብተዋል።
ብራይተን በበኩሉ ወልቭስን 3 ለ 0 በሆነ ሰፊ ውጤት ሲያሸንፍ ሂንሽልውድ፣ ሉዊስ ደንክ እና ያኩብ ሚንዝ የድል ግቦቹን ከመረብ አሳርፈዋል።
ቀደም ብሎ በአንፊልድ ስታዲየም የተደረገው የሊቨርፑል እና የቼልሲ ተጠባቂ ፍልሚያ 1 ለ 1 በሆነ አቻ ውጤት ተጠናቋል።
ለሊቨርፑል ራያን ግራቨንበርግ ግብ ሲያስቆጥር ለለንደኑ ክለብ ቼልሲ ደግሞ ኢንዞ ፈርናንዴዝ የአቻነቷን ግብ አስቆጥሯል።
ውጤቱ ቼልሲ ካጋጠሙት ተከታታይ ሽንፈቶች እንዲያገግም ሲረዳው ሊቨርፑል ግን በሻምፒዮንስ ሊግ ተሳትፎው ላይ ጥያቄ እንዲያንዣብብ አድርጎበታል።
#premierleague #footballnews #epl #sports #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
ቦርንማውዝ ፉልሃምን 1 ለ 0
ብራይተን ወልቭስን 3 ለ 0
#ethiopia | በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የ36ኛ ሳምንት መርሃ ግብር ማንቼስተር ዩናይትድ ከሜዳው ውጭ ከሰንደርላንድ ጋር ያደረገው ጨዋታ ያለ ምንም ግብ በአቻ ውጤት ተጠናቋል።
ቀይ ሰይጣኖቹ ከሦስት ተከታታይ ድሎች በኋላ ነጥብ ለመጀመሪያ ጊዜ የተጋሩበት አጋጣሚ ሆኖ ተመዝግቧል።
በሌላ በኩል ቦርንማውዝ ፉልሃምን 1 ለ 0 በሆነ ውጤት በማሸነፍ በአውሮፓ መድረክ የመሳተፍ ተስፋውን አድሷል።
በዚህ ጨዋታ ከሁለቱም ወገን አንደርሰን እና ክሪስት በፈጸሙት ጥፋት በቀይ ካርድ ከሜዳ ተሰናብተዋል።
ብራይተን በበኩሉ ወልቭስን 3 ለ 0 በሆነ ሰፊ ውጤት ሲያሸንፍ ሂንሽልውድ፣ ሉዊስ ደንክ እና ያኩብ ሚንዝ የድል ግቦቹን ከመረብ አሳርፈዋል።
ቀደም ብሎ በአንፊልድ ስታዲየም የተደረገው የሊቨርፑል እና የቼልሲ ተጠባቂ ፍልሚያ 1 ለ 1 በሆነ አቻ ውጤት ተጠናቋል።
ለሊቨርፑል ራያን ግራቨንበርግ ግብ ሲያስቆጥር ለለንደኑ ክለብ ቼልሲ ደግሞ ኢንዞ ፈርናንዴዝ የአቻነቷን ግብ አስቆጥሯል።
ውጤቱ ቼልሲ ካጋጠሙት ተከታታይ ሽንፈቶች እንዲያገግም ሲረዳው ሊቨርፑል ግን በሻምፒዮንስ ሊግ ተሳትፎው ላይ ጥያቄ እንዲያንዣብብ አድርጎበታል።
#premierleague #footballnews #epl #sports #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
3 months ago
ማንቼስተር ዩናይትድ እና ሰንደርላንድ አቻ ተለያዩ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 1፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ 36ኛ ሳምንት መርሐግብር ከሜዳው ውጭ ሰንደርላንድን የገጠመው ማንቼስተር ዩናይትድ ያለግብ አቻ ተለያይቷል።
በሌሎች ጨዋታዎች ብራይተን ወልቭስን 3 ለ 0 እንዲሁም በርንማውዝ ፉልሃምን 1 ለ 0 አሸንፈዋል፡፡
ቀደም ብሎ ቀን 8 ሰዓት ከ30 በተደረገ የሊጉ መርሐ ግብር ሊቨርፑል ከቼልሲ 1 ለ 1 አቻ ተለያይተዋል፡፡
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 1፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ 36ኛ ሳምንት መርሐግብር ከሜዳው ውጭ ሰንደርላንድን የገጠመው ማንቼስተር ዩናይትድ ያለግብ አቻ ተለያይቷል።
በሌሎች ጨዋታዎች ብራይተን ወልቭስን 3 ለ 0 እንዲሁም በርንማውዝ ፉልሃምን 1 ለ 0 አሸንፈዋል፡፡
ቀደም ብሎ ቀን 8 ሰዓት ከ30 በተደረገ የሊጉ መርሐ ግብር ሊቨርፑል ከቼልሲ 1 ለ 1 አቻ ተለያይተዋል፡፡
Sponsored by
Surafel
3 months ago
በሊጉ ዋንጫ ፉክክር ውስጥ ለመቆየትና ላለመውረድ የሚደረጉ ተጠባቂ ጨዋታዎች
የ36ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ዛሬ በሚደረጉ አምስት ጨዋታዎች መደረግ ይጀምራል፡፡
ቀን 8 ሰዓት 30 ላይ ሊቨርፑል በሜዳው አንፊልድ ሮድ ቼልሲን የሚያስተናግድበት መርሐ ግብር የዕለቱ ቀዳሚ ጨዋታ ነው፡፡
ሁለቱም ቡድኖች በአውሮፓ መድረክ የሚያሳትፋቸውን ውጤት ይዘው የውድድር ዓመቱን ለማጠናቀቅ እየተፋለሙ ይገኛል፡፡
በሊጉ ከሦስት ተከታታይ ድል በኋላ በሳምንቱ መጨረሻ በማንቼስተር ዩናይትድ ሽንፈት ያስተናገደው ሊቨርፑል ወደ ድል ለመመለስ ወደ ሜዳ ይገባል፡፡
ያለፉትን ስድስት ተከታታይ ጨዋታዎች በሊጉ የተሸነፈው ቼልሲ ወደ ድል ለመምጣት የሚያደርገው ፍልሚያ ይጠበቃል፡፡
ቼልሲ በዛሬው ጨዋታ በሊቨርፑል የሚሸነፍ ከሆነ ከ74 ዓመታት በኋላ ሰባት ተከታታይ የሊግ ጨዋታዎችን የሚሸነፍ ይሆናል፡፡
አመሻሽ 11 ሰዓት ላይ ማንቼስተር ዩናይትድ ከሜዳው ውጪ ተጉዞ ከሰንደርላንድ ጋር ጨዋታውን ያደርጋል፡፡
የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ተሳትፎውን ያረጋገጠው ማንቼስተር ዩናይትድ በሊጉ አራተኛ ተከታታይ ድሉን ለማሳካት ይፋለማል፡፡
በተመሳሳይ ሰዓት ፉልሃም ከቦርንማውዝ እንዲሁም ብራይተን ከወልቭስ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡
ምሽት 1 ሰዓት 30 ላይ ደጎሞ ማንቼስተር ሲቲ በሜዳው ኢትሃድ ከብሬንትፎርድ የሚያደርገው ጨዋታ ይጠበቃል፡፡
በ35ኛ ሳምንት የሊጉ መርሐ ግብር ነጥብ የጣለው ማንቼስተር ሲቲ የዋንጫ ፉክክሩን ለማስቀጠል ይፋለማል፡፡
ማንቼስተር ሲቲ የዛሬውን ጨዋታ የሚያሸንፍ ከሆነ አርሰናል ነገ ምሽት ጨዋታውን እስከሚያደርግ ድረስ የነጥብ ልዩነቱን ወደ ሁለት ማጥበብ ይችላል፡፡
seledadotio
seledadotio
የ36ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ዛሬ በሚደረጉ አምስት ጨዋታዎች መደረግ ይጀምራል፡፡
ቀን 8 ሰዓት 30 ላይ ሊቨርፑል በሜዳው አንፊልድ ሮድ ቼልሲን የሚያስተናግድበት መርሐ ግብር የዕለቱ ቀዳሚ ጨዋታ ነው፡፡
ሁለቱም ቡድኖች በአውሮፓ መድረክ የሚያሳትፋቸውን ውጤት ይዘው የውድድር ዓመቱን ለማጠናቀቅ እየተፋለሙ ይገኛል፡፡
በሊጉ ከሦስት ተከታታይ ድል በኋላ በሳምንቱ መጨረሻ በማንቼስተር ዩናይትድ ሽንፈት ያስተናገደው ሊቨርፑል ወደ ድል ለመመለስ ወደ ሜዳ ይገባል፡፡
ያለፉትን ስድስት ተከታታይ ጨዋታዎች በሊጉ የተሸነፈው ቼልሲ ወደ ድል ለመምጣት የሚያደርገው ፍልሚያ ይጠበቃል፡፡
ቼልሲ በዛሬው ጨዋታ በሊቨርፑል የሚሸነፍ ከሆነ ከ74 ዓመታት በኋላ ሰባት ተከታታይ የሊግ ጨዋታዎችን የሚሸነፍ ይሆናል፡፡
አመሻሽ 11 ሰዓት ላይ ማንቼስተር ዩናይትድ ከሜዳው ውጪ ተጉዞ ከሰንደርላንድ ጋር ጨዋታውን ያደርጋል፡፡
የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ተሳትፎውን ያረጋገጠው ማንቼስተር ዩናይትድ በሊጉ አራተኛ ተከታታይ ድሉን ለማሳካት ይፋለማል፡፡
በተመሳሳይ ሰዓት ፉልሃም ከቦርንማውዝ እንዲሁም ብራይተን ከወልቭስ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡
ምሽት 1 ሰዓት 30 ላይ ደጎሞ ማንቼስተር ሲቲ በሜዳው ኢትሃድ ከብሬንትፎርድ የሚያደርገው ጨዋታ ይጠበቃል፡፡
በ35ኛ ሳምንት የሊጉ መርሐ ግብር ነጥብ የጣለው ማንቼስተር ሲቲ የዋንጫ ፉክክሩን ለማስቀጠል ይፋለማል፡፡
ማንቼስተር ሲቲ የዛሬውን ጨዋታ የሚያሸንፍ ከሆነ አርሰናል ነገ ምሽት ጨዋታውን እስከሚያደርግ ድረስ የነጥብ ልዩነቱን ወደ ሁለት ማጥበብ ይችላል፡፡
seledadotio
seledadotio
3 months ago
ማንችስተር ሲቲ ከ ብሬንትፎርድ፣ ሊቨርፑል ከ ቼልሲ
*************
በ36ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬ ምሽት 1 ሰዓት ከ30 ላይ ማንችስተር ሲቲ ብሬንትፎርድን ያስተናግዳል። ከኤቨርተን ጋር ነጥብ መጋራቱን ተከትሎ የሊጉን ዋንጫ የማንሳት ዕድሉ ሙሉ በሙሉ ከእጁ የወጣው ማንችስተር ሲቲ፣ አሁንም ያለውን ጥቂት ዕድል ለመጠቀም እና በአርሰናል ላይ ጫና ለማሳደር ወደ ሜዳ ይገባል።
ሆኖም ዘንድሮ ጠንካራ የውድድር ጊዜ ያሳለፈው ብሬንትፎርድ፣ የአውሮፓ መድረክ ተሳትፎን ለማግኘት እየታገለ በመሆኑ ጨዋታው ለሲቲ እጅግ ፈታኝ እንደሚሆን ይጠበቃል። በተለይ ክሪስታል ፓላስ እና አስቶን ቪላ በዩሮፓ ሊግ እና በኮንፈረንስ ሊግ ለፍጻሜ መድረሳቸውን ተከትሎ፣ በቀጣይ ዓመት በአውሮፓ መድረክ የሚሳተፉ የእንግሊዝ ክለቦች ቁጥር ሊጨምር ስለሚችል በ51 ነጥብ 7ኛ ደረጃ ላይ የተቀመጠው ብሬንትፎርድ ይህንን አጋጣሚ ለመጠቀም ይፋለማል።
በኢትሃድ ስታዲየም በሚደረገው ጨዋታ ሮድሪ ለዛሬው ፍልሚያ ሊደርስ እንደሚችል አሰልጣኝ ፔፕ ጋርዲዮላ ተናግሯል። ጋርዲዮላ ትላንት በሰጠት መግለጫ "በዛሬው ጨዋታ ከተሸነፍን የዋንጫው ጉዞ በይፋ ያበቃል" ሲል የጨዋታውን ወሳኝነት ገልቷል። ሲቲ ካሸነፈ ከአርሰናል ያለውን የነጥብ ልዩነት ወደ ሁለት የሚያጠብ ይሆናል፡፡
ቀን 8 ሰዓት ከ30 ላይ ደግሞ ሊቨርፑል እና ቼልሲ የሚገናኙበት ጨዋታ ይጠበቃል። በፕሪሚየር ሊጉ ያለፉትን ስድስት ተከታታይ ጨዋታዎች የተሸነፈው ቼልሲ፣ ዛሬም በአንፊልድ ሌላ ከባድ ፈተና ይጠብቀዋል። ሊጉ ሊጠናቀቅ ሦስት ጨዋታዎች ብቻ እየቀሩት እስካሁን የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ተሳትፎውን ያላረጋገጠው ሊቨርፑል፣ ከዛሬው ጨዋታ ሦስት ነጥብ ካገኘ መሳተፉን በይፋ የሚያረጋግጥ ይሆናል። በአንፊልድ በሚደረገው ጨዋታ ሞሃመድ ሳላህ እና አሊሰን ቤከር አሁንም በጉዳት ከስብስቡ ውጭ ናቸው። በቼልሲ በኩል ሌቪ ኮልዊል እና ሬስ ጄምስ ለጨዋታው ሊደርሱ ይችላሉ ተብሏል።
በሻምፒዮንስ ሊግ መሳተፉን ቀድሞ ያረጋገጠመው ማንችስተር ዩናይትድ ከ ሜዳው ወጭ ከሰንደርላንድ 11 ሰዓት ላይ ጨዋታውን ያደርጋል፡፡ ብራይተን ከ ዎልቭስ እና ፉልሀም ከ ቦርንማውዝ ሌሎች ዛሬ የሚደረጉ ጨዋታዎች ናቸው፡፡
በአንተነህ ሲሳይ
*************
በ36ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬ ምሽት 1 ሰዓት ከ30 ላይ ማንችስተር ሲቲ ብሬንትፎርድን ያስተናግዳል። ከኤቨርተን ጋር ነጥብ መጋራቱን ተከትሎ የሊጉን ዋንጫ የማንሳት ዕድሉ ሙሉ በሙሉ ከእጁ የወጣው ማንችስተር ሲቲ፣ አሁንም ያለውን ጥቂት ዕድል ለመጠቀም እና በአርሰናል ላይ ጫና ለማሳደር ወደ ሜዳ ይገባል።
ሆኖም ዘንድሮ ጠንካራ የውድድር ጊዜ ያሳለፈው ብሬንትፎርድ፣ የአውሮፓ መድረክ ተሳትፎን ለማግኘት እየታገለ በመሆኑ ጨዋታው ለሲቲ እጅግ ፈታኝ እንደሚሆን ይጠበቃል። በተለይ ክሪስታል ፓላስ እና አስቶን ቪላ በዩሮፓ ሊግ እና በኮንፈረንስ ሊግ ለፍጻሜ መድረሳቸውን ተከትሎ፣ በቀጣይ ዓመት በአውሮፓ መድረክ የሚሳተፉ የእንግሊዝ ክለቦች ቁጥር ሊጨምር ስለሚችል በ51 ነጥብ 7ኛ ደረጃ ላይ የተቀመጠው ብሬንትፎርድ ይህንን አጋጣሚ ለመጠቀም ይፋለማል።
በኢትሃድ ስታዲየም በሚደረገው ጨዋታ ሮድሪ ለዛሬው ፍልሚያ ሊደርስ እንደሚችል አሰልጣኝ ፔፕ ጋርዲዮላ ተናግሯል። ጋርዲዮላ ትላንት በሰጠት መግለጫ "በዛሬው ጨዋታ ከተሸነፍን የዋንጫው ጉዞ በይፋ ያበቃል" ሲል የጨዋታውን ወሳኝነት ገልቷል። ሲቲ ካሸነፈ ከአርሰናል ያለውን የነጥብ ልዩነት ወደ ሁለት የሚያጠብ ይሆናል፡፡
ቀን 8 ሰዓት ከ30 ላይ ደግሞ ሊቨርፑል እና ቼልሲ የሚገናኙበት ጨዋታ ይጠበቃል። በፕሪሚየር ሊጉ ያለፉትን ስድስት ተከታታይ ጨዋታዎች የተሸነፈው ቼልሲ፣ ዛሬም በአንፊልድ ሌላ ከባድ ፈተና ይጠብቀዋል። ሊጉ ሊጠናቀቅ ሦስት ጨዋታዎች ብቻ እየቀሩት እስካሁን የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ተሳትፎውን ያላረጋገጠው ሊቨርፑል፣ ከዛሬው ጨዋታ ሦስት ነጥብ ካገኘ መሳተፉን በይፋ የሚያረጋግጥ ይሆናል። በአንፊልድ በሚደረገው ጨዋታ ሞሃመድ ሳላህ እና አሊሰን ቤከር አሁንም በጉዳት ከስብስቡ ውጭ ናቸው። በቼልሲ በኩል ሌቪ ኮልዊል እና ሬስ ጄምስ ለጨዋታው ሊደርሱ ይችላሉ ተብሏል።
በሻምፒዮንስ ሊግ መሳተፉን ቀድሞ ያረጋገጠመው ማንችስተር ዩናይትድ ከ ሜዳው ወጭ ከሰንደርላንድ 11 ሰዓት ላይ ጨዋታውን ያደርጋል፡፡ ብራይተን ከ ዎልቭስ እና ፉልሀም ከ ቦርንማውዝ ሌሎች ዛሬ የሚደረጉ ጨዋታዎች ናቸው፡፡
በአንተነህ ሲሳይ
3 months ago
በሊጉ የዋንጫ ፉክክር ውስጥ ለመቆየትና ላለመውረድ የሚደረጉ ተጠባቂ የሊጉ ጨዋታዎች
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 1፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የ36ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ዛሬ በሚደረጉ አምስት ጨዋታዎች መደረግ ይጀምራል፡፡
ቀን 8 ሰዓት 30 ላይ ሊቨርፑል በሜዳው አንፊልድ ሮድ ቼልሲን የሚያስተናግድበት መርሐ ግብር የዕለቱ ቀዳሚ ጨዋታ ነው፡፡
ሁለቱም ቡድኖች በአውሮፓ መድረክ የሚያሳትፋቸውን ውጤት ይዘው የውድድር ዓመቱን ለማጠናቀቅ እየተፋለሙ ይገኛል፡፡
በሊጉ ከሦስት ተከታታይ ድል በኋላ በሳምንቱ መጨረሻ በማንቼስተር ዩናይትድ ሽንፈት ያስተናገደው ሊቨርፑል ወደ ድል ለመመለስ ወደ ሜዳ ይገባል፡፡
ያለፉትን ስድስት ተከታታይ ጨዋታዎች በሊጉ የተሸነፈው ቼልሲ ወደ ድል ለመምጣት የሚያደርገው ፍልሚያ ይጠበቃል፡፡
ቼልሲ በዛሬው ጨዋታ በሊቨርፑል የሚሸነፍ ከሆነ ከ74 ዓመታት በኋላ ሰባት ተከታታይ የሊግ ጨዋታዎችን የሚሸነፍ ይሆናል፡፡
ሁለቱ ቡድኖች እርስበርስ ካደረጓቸው ያለፉት አምስት ጨዋታዎች ሊቨርፑል በሦስቱ ሲያሸንፍ ቼልሲ በሁለቱ ድል አድርጓል፡፡
አመሻሽ 11 ሰዓት ላይ ማንቼስተር ዩናይትድ ከሜዳው ውጪ ተጉዞ ከሰንደርላንድ ጋር ጨዋታውን ያደርጋል፡፡
የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ተሳትፎውን ያረጋገጠው ማንቼስተር ዩናይትድ በሊጉ አራተኛ ተከታታይ ድሉን ለማሳካት ይፋለማል፡፡
ሰንደርላንድ በበኩሉ ከተከታታይ ሦስት ጨዋታዎች ድል አልባ ጉዞ በኋላ ወደ ድል ለመመለስ ወደ ሜዳ የሚገባ ይሆናል፡፡
ሁለቱ ቡድኖች እርስበርስ ካደረጓቸው ያለፉት አምስት ጨዋታዎች ማንቼስተር ዩናይትድ አራቱን በማሸነፍ የበላይነቱን ሲይዝ ሰንደርላንድ በአንዱ ድል አድርጓል፡፡
በተመሳሳይ ሰዓት ፉልሃም ከቦርንማውዝ እንዲሁም ብራይተን ከወልቭስ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡
ምሽት 1 ሰዓት 30 ላይ ማንቼስተር ሲቲ በሜዳው ኢትሃድ ከብሬንትፎርድ የሚያደርገው ጨዋታ ይጠበቃል፡፡
በ35ኛ ሳምንት የሊጉ መርሐ ግብር ነጥብ የጣለው ማንቼስተር ሲቲ የዋንጫ ፉክክሩን ለማጠናከር ይፋለማል፡፡
ማንቼስተር ሲቲ የዛሬውን ጨዋታ የሚያሸንፍ ከሆነ አርሰናል ነገ ምሽት ጨዋታውን እስከሚያደርግ ድረስ የነጥብ ልዩነቱን ወደ ሁለት ማጥበብ ይችላል፡፡
የሊጉ ጨዋታ ነገ ሲቀጥል የሊጉ መሪ አርሰናል ከሜዳው ውጪ ተጉዞ ምሽት 12 ሰዓት 30 ላይ ከዌስትሃም ዩናይትድ ጋር ይጫወታል፡፡
የሊጉ መሪ አርሰናል መሪነቱን ለማጠናከር እና ዋንጫውን ለማንሳት የሚያደርገውን ጉዞ አጠናክሮ ለመቀጠል ይፋለማል፡፡
ተጋጣሚው ዌስትሃም ዩናይትድ በበኩሉ ላለመውረድ የሚያደርገው ብርቱ ፉክክር ተጠባቂ ነው፡፡
ኖቲንግሃም ፎረስት ከኒውካስል ዩናይትድ፣ ክሪስታል ፓላስ ከኤቨርተን እንዲሁም በርንሌይ ከአስቶንቪላ በዕለቱ በተመሳሳይ ሰዓት ቀን 10 ሰዓት ላይ የሚደረጉ ጨዋታዎች ናቸው፡፡
የ36ኛ ሳምንት የሊጉ መርሐ ግብር ሰኞ ምሽት 4 ሰዓት ላይ ቶተንሃም ሆትስፐር ከሊድስ ዩናይትድ በሚያደርጉት ጨዋታ ይጠናቀቃል፡፡
ሊጉን አርሰናል በ76 ነጥብ ሲመራ ማንቼስተር ሲቲ 71፣ ማንቼስተር ዩናይትድ 64 እንዲሁም ሊቨርፑል በ58 ነጥብ ከ2ኛ እስከ 4ኛ ያለውን ደረጃ ይዘዋል፡፡
ኤርሊንግ ብራውት ሃላንድ በ25 ግቦች የሊጉን ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነት ደረጃ ሲመራ ኢጎር ቲያጎ በ22 ግቦች ይከተላል፡፡
በወንድማገኝ ጸጋዬ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 1፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የ36ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ዛሬ በሚደረጉ አምስት ጨዋታዎች መደረግ ይጀምራል፡፡
ቀን 8 ሰዓት 30 ላይ ሊቨርፑል በሜዳው አንፊልድ ሮድ ቼልሲን የሚያስተናግድበት መርሐ ግብር የዕለቱ ቀዳሚ ጨዋታ ነው፡፡
ሁለቱም ቡድኖች በአውሮፓ መድረክ የሚያሳትፋቸውን ውጤት ይዘው የውድድር ዓመቱን ለማጠናቀቅ እየተፋለሙ ይገኛል፡፡
በሊጉ ከሦስት ተከታታይ ድል በኋላ በሳምንቱ መጨረሻ በማንቼስተር ዩናይትድ ሽንፈት ያስተናገደው ሊቨርፑል ወደ ድል ለመመለስ ወደ ሜዳ ይገባል፡፡
ያለፉትን ስድስት ተከታታይ ጨዋታዎች በሊጉ የተሸነፈው ቼልሲ ወደ ድል ለመምጣት የሚያደርገው ፍልሚያ ይጠበቃል፡፡
ቼልሲ በዛሬው ጨዋታ በሊቨርፑል የሚሸነፍ ከሆነ ከ74 ዓመታት በኋላ ሰባት ተከታታይ የሊግ ጨዋታዎችን የሚሸነፍ ይሆናል፡፡
ሁለቱ ቡድኖች እርስበርስ ካደረጓቸው ያለፉት አምስት ጨዋታዎች ሊቨርፑል በሦስቱ ሲያሸንፍ ቼልሲ በሁለቱ ድል አድርጓል፡፡
አመሻሽ 11 ሰዓት ላይ ማንቼስተር ዩናይትድ ከሜዳው ውጪ ተጉዞ ከሰንደርላንድ ጋር ጨዋታውን ያደርጋል፡፡
የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ተሳትፎውን ያረጋገጠው ማንቼስተር ዩናይትድ በሊጉ አራተኛ ተከታታይ ድሉን ለማሳካት ይፋለማል፡፡
ሰንደርላንድ በበኩሉ ከተከታታይ ሦስት ጨዋታዎች ድል አልባ ጉዞ በኋላ ወደ ድል ለመመለስ ወደ ሜዳ የሚገባ ይሆናል፡፡
ሁለቱ ቡድኖች እርስበርስ ካደረጓቸው ያለፉት አምስት ጨዋታዎች ማንቼስተር ዩናይትድ አራቱን በማሸነፍ የበላይነቱን ሲይዝ ሰንደርላንድ በአንዱ ድል አድርጓል፡፡
በተመሳሳይ ሰዓት ፉልሃም ከቦርንማውዝ እንዲሁም ብራይተን ከወልቭስ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡
ምሽት 1 ሰዓት 30 ላይ ማንቼስተር ሲቲ በሜዳው ኢትሃድ ከብሬንትፎርድ የሚያደርገው ጨዋታ ይጠበቃል፡፡
በ35ኛ ሳምንት የሊጉ መርሐ ግብር ነጥብ የጣለው ማንቼስተር ሲቲ የዋንጫ ፉክክሩን ለማጠናከር ይፋለማል፡፡
ማንቼስተር ሲቲ የዛሬውን ጨዋታ የሚያሸንፍ ከሆነ አርሰናል ነገ ምሽት ጨዋታውን እስከሚያደርግ ድረስ የነጥብ ልዩነቱን ወደ ሁለት ማጥበብ ይችላል፡፡
የሊጉ ጨዋታ ነገ ሲቀጥል የሊጉ መሪ አርሰናል ከሜዳው ውጪ ተጉዞ ምሽት 12 ሰዓት 30 ላይ ከዌስትሃም ዩናይትድ ጋር ይጫወታል፡፡
የሊጉ መሪ አርሰናል መሪነቱን ለማጠናከር እና ዋንጫውን ለማንሳት የሚያደርገውን ጉዞ አጠናክሮ ለመቀጠል ይፋለማል፡፡
ተጋጣሚው ዌስትሃም ዩናይትድ በበኩሉ ላለመውረድ የሚያደርገው ብርቱ ፉክክር ተጠባቂ ነው፡፡
ኖቲንግሃም ፎረስት ከኒውካስል ዩናይትድ፣ ክሪስታል ፓላስ ከኤቨርተን እንዲሁም በርንሌይ ከአስቶንቪላ በዕለቱ በተመሳሳይ ሰዓት ቀን 10 ሰዓት ላይ የሚደረጉ ጨዋታዎች ናቸው፡፡
የ36ኛ ሳምንት የሊጉ መርሐ ግብር ሰኞ ምሽት 4 ሰዓት ላይ ቶተንሃም ሆትስፐር ከሊድስ ዩናይትድ በሚያደርጉት ጨዋታ ይጠናቀቃል፡፡
ሊጉን አርሰናል በ76 ነጥብ ሲመራ ማንቼስተር ሲቲ 71፣ ማንቼስተር ዩናይትድ 64 እንዲሁም ሊቨርፑል በ58 ነጥብ ከ2ኛ እስከ 4ኛ ያለውን ደረጃ ይዘዋል፡፡
ኤርሊንግ ብራውት ሃላንድ በ25 ግቦች የሊጉን ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነት ደረጃ ሲመራ ኢጎር ቲያጎ በ22 ግቦች ይከተላል፡፡
በወንድማገኝ ጸጋዬ
Comments