2 hours ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የመናዊያን በዝቅተኛ ደመወዝ በሚቀጠሩ ኢትዮጵያዊያን መማረራቸውን ገለፁ፡፡ እድሜው በ30ዎቹ ውስጥ የሚገኘው ዛሂድ አል ዛቢዲ አምስት ቤተሰቦቹን ለመርዳት ያገኘውን ሲሰራ መቆየቱን ይናገራል፡፡ ለሚድል ኢስት ሞኒተር ሲናገር ‹‹ለ15 አመታት ያህል በሬስቶራንቶች ሰሀን በማጠብና ቤት በማፅዳት ስራ ተሰማርቼ ቆይቻለሁ፡፡ የምችለው ስራም ይህ ብቻ ነው›› ብሏል፡፡ ጨምሮም ‹‹በፊት በቀላሉ ስራ አገኝ ነበር፡፡ አሁን ግን ስራ ማግኘት ከባድ ሆኗል›› ያል ዛቢዲ የዛሬ 7 አመት የተሻለ ገቢ ለማግኘት ወደአደን መሄዱን ገልጿል፡፡ በሚሰራው የቀን ስራ ኑሮውን እየደገፈ መቆየቱን ጠቅሷል፡፡ ሲቀጥልም ‹‹እኔ በአደን በርካታ ሬስቶራንቶች ውስጥ ስሰራ ነበር፡፡ ነገር ግን አሁን ከቀን ወደቀን ሁኔታው እየባሰበት ሄዷል፡፡
ምክንያቱም ሬስቶራንቶች የሚፈልጉት ኢትዮጵያዊያን ሰራተኞችን ነው፡፡ ኢትዮጵያዊያኑ በማንኛውም ክፍያ ለመስራት ፈቃደኛ በመሆናቸው ሬስቶራንቶቹ የሚመርጡት እነሱን ነው›› ብሏል፡፡ አል ዛቢዲ እንደሚለው በፊት ይከፈለው የነበረው 130,00 የየመን ሪያል ወይንም 83 ዶላር ገደማ ነበር፡፡ ኢትዮጵያዊያን ግን እሱ የሚሰራውን ስራ በ80,000 ሪያል ወይንም በ51 ዶላር ተቀብለው እንደሚሰሩ አስረድቷል፡፡
ለኢትዮጵያዊያኑ የሚከፈለውን ደመወዝ ተቀብሎ ቤተሰቡን ማስተዳደር እንደማይችልም አስታውቋል፡፡ ሲናገርም ‹‹ኢትዮጵያዊያን እዚህ ምንም ቤተሰብ የላቸውም፡፡ በማንኛውም ገንዘብ ተቀጥረው ቢሰሩ ህይወታቸውን መምራት ያስችላቸዋል፡፡ እኔ ቤተሰቤን የማስተዳድርበትን ስራ እነሱ እየወሰዱብኝ ነው›› ሲልም አስረድቷል፡፡ ለጋዜጣው አስተያየት የሰጡና ስማቸው እንዲጠቀስ ያልፈለጉ ኢትዮጵያዊያን በዝቅተኛ ደመወዝ የሚቀጠሩት በየመን የመቆየት እቅድ ስለሌላቸው እንደሆነ ገልፀዋል፡፡ ዋነኛ አላማቸው ሳኡዲ አረቢያ መግባት መሆኑን የጠቀሱት ስደተኞቹ ስራ የሚሰሩት የቀን መሰረታዊ ፍላጎታቸውን ለማሟላት ብቻ መሆኑን መናገራቸውን ዘገባው አስታውቋል፡፡
ምክንያቱም ሬስቶራንቶች የሚፈልጉት ኢትዮጵያዊያን ሰራተኞችን ነው፡፡ ኢትዮጵያዊያኑ በማንኛውም ክፍያ ለመስራት ፈቃደኛ በመሆናቸው ሬስቶራንቶቹ የሚመርጡት እነሱን ነው›› ብሏል፡፡ አል ዛቢዲ እንደሚለው በፊት ይከፈለው የነበረው 130,00 የየመን ሪያል ወይንም 83 ዶላር ገደማ ነበር፡፡ ኢትዮጵያዊያን ግን እሱ የሚሰራውን ስራ በ80,000 ሪያል ወይንም በ51 ዶላር ተቀብለው እንደሚሰሩ አስረድቷል፡፡
ለኢትዮጵያዊያኑ የሚከፈለውን ደመወዝ ተቀብሎ ቤተሰቡን ማስተዳደር እንደማይችልም አስታውቋል፡፡ ሲናገርም ‹‹ኢትዮጵያዊያን እዚህ ምንም ቤተሰብ የላቸውም፡፡ በማንኛውም ገንዘብ ተቀጥረው ቢሰሩ ህይወታቸውን መምራት ያስችላቸዋል፡፡ እኔ ቤተሰቤን የማስተዳድርበትን ስራ እነሱ እየወሰዱብኝ ነው›› ሲልም አስረድቷል፡፡ ለጋዜጣው አስተያየት የሰጡና ስማቸው እንዲጠቀስ ያልፈለጉ ኢትዮጵያዊያን በዝቅተኛ ደመወዝ የሚቀጠሩት በየመን የመቆየት እቅድ ስለሌላቸው እንደሆነ ገልፀዋል፡፡ ዋነኛ አላማቸው ሳኡዲ አረቢያ መግባት መሆኑን የጠቀሱት ስደተኞቹ ስራ የሚሰሩት የቀን መሰረታዊ ፍላጎታቸውን ለማሟላት ብቻ መሆኑን መናገራቸውን ዘገባው አስታውቋል፡፡
4 hours ago
ቮሎዲሚር ዘለንስኪ ከቭላድሚር ፑቲን ጋር በአካል ለመወያየት ጥሪ አቀረቡ
#ethiopia | ዩክሬንና ሩሲያ በቀጥታ በመገናኘት ጦርነቱን እንዲያቆሙ የዩክሬኑ ፕሬዚዳንት ቮሎዲሚር ዘለንስኪ (ቪዲዮ) ለሩሲያው ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን በጻፉት ግልጽ ደብዳቤ በአካል ለመገናኘት ጥሪ ማቅረባቸው ተሰማ።
የአሜሪካ ትኩረት ሙሉ በሙሉ ወደ ኢራን ጉዳይ በዞረበት በዚህ ወቅት፣ ጦርነቱ እንደገና የአሜሪካ ቀዳሚ አጀንዳ እስኪሆን ድረስ ዝም ብሎ መጠበቅ ስህተት መሆኑን እና ሰላም ሊመጣ የሚችለው በሁለቱ አገራት ቀጥተኛ ንግግር ብቻ መሆኑን ፕሬዚዳንቱ ገልጸዋል።
ቮሎዲሚር ዘለንስኪ ለሚካሄደው ድርድር እንዲረዳ ሙሉ የተኩስ አቁም እንዲታወጅ የጠየቁ ቢሆንም፣ ቭላድሚር ፑቲን ግን ከዚህ ቀደም የተኩስ አቁም ጥያቄውን ውድቅ አድርገውታል።
የክሬምሊን ቤተ መንግሥት ደብዳቤው እንደደረሰውና ለፑቲን ገለጻ እንደሚደረግላቸው ያረጋገጠ ሲሆን፣ ከዚህ ቀደም ሩሲያ ዘለንስኪ ወደ ሞስኮ መጥተው መወያየት እንደሚችሉ ገልጻ ነበር።
ቭላድሚር ፑቲን ስምምነት ለማድረግ ፈቃደኛ መሆናቸውን ቢናገሩም፣ ዩክሬን ዶኔትስክ፣ ሉሃንስክ፣ ኬርሰን እና ዛፖሪዢያ ከተባሉ አራት ክልሎች እንድትወጣ እና የኔቶ አባል የመሆን ጥረቷን እንድታቆም የሚሉትን ጠንካራ ቅድመ ሁኔታዎችን አስቀምጠዋል፡፡
ዩክሬን ግን ይህንን ግዛቶቿን አሳልፋ መስጠት የሩሲያን ዳግም ወረራ የሚያበረታታ መሆኑን በመግለጽ የሩሲያን ቅድመ ሁኔታዎች ሙሉ በሙሉ ውድቅ አድርጋለች።
በሌላ በኩል የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ የሁለቱ መሪዎች መገናኘት "በጣም ጥሩ ነገር ነው" ሲሉ ድጋፋቸውን ሰጥተዋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጋዜጣ + #russian #uk #peace #nowar
#ethiopia | ዩክሬንና ሩሲያ በቀጥታ በመገናኘት ጦርነቱን እንዲያቆሙ የዩክሬኑ ፕሬዚዳንት ቮሎዲሚር ዘለንስኪ (ቪዲዮ) ለሩሲያው ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን በጻፉት ግልጽ ደብዳቤ በአካል ለመገናኘት ጥሪ ማቅረባቸው ተሰማ።
የአሜሪካ ትኩረት ሙሉ በሙሉ ወደ ኢራን ጉዳይ በዞረበት በዚህ ወቅት፣ ጦርነቱ እንደገና የአሜሪካ ቀዳሚ አጀንዳ እስኪሆን ድረስ ዝም ብሎ መጠበቅ ስህተት መሆኑን እና ሰላም ሊመጣ የሚችለው በሁለቱ አገራት ቀጥተኛ ንግግር ብቻ መሆኑን ፕሬዚዳንቱ ገልጸዋል።
ቮሎዲሚር ዘለንስኪ ለሚካሄደው ድርድር እንዲረዳ ሙሉ የተኩስ አቁም እንዲታወጅ የጠየቁ ቢሆንም፣ ቭላድሚር ፑቲን ግን ከዚህ ቀደም የተኩስ አቁም ጥያቄውን ውድቅ አድርገውታል።
የክሬምሊን ቤተ መንግሥት ደብዳቤው እንደደረሰውና ለፑቲን ገለጻ እንደሚደረግላቸው ያረጋገጠ ሲሆን፣ ከዚህ ቀደም ሩሲያ ዘለንስኪ ወደ ሞስኮ መጥተው መወያየት እንደሚችሉ ገልጻ ነበር።
ቭላድሚር ፑቲን ስምምነት ለማድረግ ፈቃደኛ መሆናቸውን ቢናገሩም፣ ዩክሬን ዶኔትስክ፣ ሉሃንስክ፣ ኬርሰን እና ዛፖሪዢያ ከተባሉ አራት ክልሎች እንድትወጣ እና የኔቶ አባል የመሆን ጥረቷን እንድታቆም የሚሉትን ጠንካራ ቅድመ ሁኔታዎችን አስቀምጠዋል፡፡
ዩክሬን ግን ይህንን ግዛቶቿን አሳልፋ መስጠት የሩሲያን ዳግም ወረራ የሚያበረታታ መሆኑን በመግለጽ የሩሲያን ቅድመ ሁኔታዎች ሙሉ በሙሉ ውድቅ አድርጋለች።
በሌላ በኩል የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ የሁለቱ መሪዎች መገናኘት "በጣም ጥሩ ነገር ነው" ሲሉ ድጋፋቸውን ሰጥተዋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጋዜጣ + #russian #uk #peace #nowar
5 hours ago
ጽንፈኝነት በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም!
የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ
የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት
Federal Democratic Republic of Ethiopia
OFFICE OF THE PRIME MINISTER
ጋዜጣዊ መግለጫ
ግንቦት 28 ቀን 2018 ዓ.ም
አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ
ወቅታዊ ጉዳዮችን አስመልክቶ የተሰጠ መግለጫ
#ethiopia | ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. ማለዳ ላይ፤ የመጀመሪያው የወገግታ ጭላንጭል በከፍታማዎቹ የኢትዮጵያ ተራሮች ላይ ፈንጥቆ ጨለማውን ሳይቀድ በፊት ኢትዮጵያውያን ረጃጅም ሰልፍ ተሰልፈዋል። በጅማ፣ በድሬዳዋ፣ በሐዋሳ፣ በባሕር ዳር እንዲሁም ስማቸው በዓለም አቀፍ የዜና ጋዜጣዎች ላይ ፈጽሞ ሊወጣ በማይችሉ ከተሞችና መንደሮች ውስጥ ያሉ ወንዶችና ሴቶች፤ ወሳኝ ተግባር ለመፈጸም በሰልፍ ቆሙ። ድምፅ ሰጡ! ይህንን ታሪካዊ ኃላፊነት ለመወጣት ከሃምሳ አራት ሚልዮን በላይ የሚሆኑ ዜጎች ተመዝግበው ነበር። ይህ ቁጥር ከአንዳንድ ሀገሮች አጠቃላይ ሕዝብ ቁጥር በላይ ነው። ይህ ምርጫ እውነተኛ ስለመሆኑ ጥያቄ ለሚያነሣ ለማንኛውም አካል ግልጽ እና የማያሻማ ምላሽ ሰጥቷል!
የኢትዮጵያ ሕዝብ ፍላጎት
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከ52,000 ምርጫ ጣቢያዎች መካከል ከ50,188 በላይ የሚሆኑት በሰዓቱ ተከፍተው ቀኑን ሙሉ መራጮችን ሲያስተናግዱ እንደነበር አረጋግጧል። ከ42 የፖለቲካ ፓርቲዎች የተወጣጡ ከ10,438 በላይ ዕጩዎች እና 80 የግል እጩዎች በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እና የክልል ምክር ቤት ወንበሮችን ለማሸነፍ ተወዳድረዋል። ይህ በማንኛውም ሊለካ በሚችል መሥፈርት በኢትዮጵያ ታሪክ ትልቁ እና በውሳኔ አሰጣጥም ሆነ በአስተዳደራዊ ረገድ እጅግ በረቀቀ ሁኔታ ተግባራዊ የተደረገ ዴሞክራሲያዊ ተሳትፎ የታየበት ኩነት ነበር።
የቀድሞው የኬንያ ፕሬዚዳንት ክቡር ኡሁሩ ኬንያታ የሚመሩትና ከ37 የአፍሪካ ሀገሮች የተወጣጡ 83 ታዛቢዎችን ያቀፈው የአፍሪካ ኅብረት የምርጫ ታዛቢ ቡድን ምርጫውን “ዲሞክራሲያዊ አስተዳደርን በሰፊው በሚደግፍ ሕጋዊና ተቋማዊ ማዕቀፍ ውስጥ የተካሄደ” ሲል ገምግሞታል።
በቀድሞዋ የኡጋንዳ ምክትል ፕሬዚዳንት ክቡር ዶክተር ስፔሲዮዛ ዋንዲራ ካዚብዌ የሚመራው የኢጋድ የምርጫ ታዛቢ ቡድን ባወጣው የመጀመሪያ ደረጃ ሪፖርት፤ በታዘቡባቸው ጣቢያዎች ሁሉ የምርጫ ሳጥኖች በትክክል የታሸጉ መሆናቸውን፣ የፓርቲ ወኪሎች በሂደቱ በሙሉ መገኘታቸውን እንዲሁም ምርጫው አስደናቂ ተቋማዊ፣ አስተዳደራዊና የቴክኖሎጂ ዕድገትን ያሳየ መሆናቸውን አረጋግጧል። የኢጋድ የምርጫ ታዛቢ ልዑክ ይህንን ምርጫ “የበርካታ አዳዲስ ምዕራፎች ምርጫ” ሲል ሰይሞታል።
የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን በድምፅ መስጠት ሂደት ውስጥ ምንም ዓይነት የሰብዓዊ መብት ጥሰት እንዳልተመለከተ አረጋግጧል። የሲቪክ ማኅበረሰብ ታዛቢዎች ጥምረት በምርጫ ቦርድ ዕውቅና ከተሰጧቸው 55 ድርጅቶች 65,299 ታዛቢዎችን በመላ ሀገሪቱ ያሠማራ ሲሆን፤ 99 በመቶ የምርጫ ጣቢያዎች ላይ ያለምንም ዕንቅፋት የመታዘብ ዕድል ማግኘቱን አረጋግጧል። እነዚህ ተዓማኒነት ያላቸው ሀገራዊ እና አኅጉራዊ ተቋማት ያደረጓቸው ግምገማዎችና የሰጧቸው እውነተኛ ፍርዶች ናቸው። እነዚህ ለአፍሪካ ጥላቻ ካላቸው ወይም የአፍሪካን ዴሞክራሲ በውጫዊ መሥፈርቶች ከሚለኩ ተቋማት የተደመጡ ድምፆች አይደሉም።
አንዳንድ ዓለም አቀፍ ተንታኞች ይህንን ምርጫ እንደ ንግሥና በዓል አድርገው ያቆሸሹት ሲሆን ውጤቱም አስቀድሞ የተወሰነ ድራማ እንደነበር አድርገው ሊያቀርቡት ሞክረዋል። እነዚህን መግለጫዎች ከአውነታው የራቁ፣ በጥናትና ትንተና ላይ ያልተመሠረቱ እንዲሁም ነፃና የታሰበበት ዲሞክራሲያዊ ምርጫቸውን በኩራት ላደረጉ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን ክብር የማይሰጡ በመሆናቸው የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ሙሉ በሙሉ የማይቀበላቸው መሆኑን ያረግጣል። አስቀድሞ የተወሰነ ውጤት ቢኖር ኖሮ፤ ከ37 የአፍሪካ ሀገሮች የተወጣጡ 83 ገለልተኛ ታዛቢዎችን፣ 65,299 የሀገር ውስጥ የሲቪል ማኅበረሰብ ታዛቢዎችን ወይም 1,100 ዕውቅና የተሰጣቸውን የዓለም አቀፍ ጋዜጠኞችን መጋበዝ ባላስፈለገ ነበር።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በዚህ ሀገራዊ ምርጫ ለተሳተፉ የኢትዮጵያ ዜጎች፤ ለብሔራዊ ምርጫ ቦርድ እና ላሠማራቸው ከ350,000 በላይ ኃላፊዎች፤ ሂደቱን ለመጠበቅ የጸጥታ ኃይሎች እንዲሁም ኢትዮጵያ ለዲሞክራሲ ግንባታ መጎልበት እና ለሂደቱ መሳካት ያላትን ቁርጠኝነት ላረጋገጡት የአፍሪካ እና ቀጠናዊ የታዛቢ ቡድኖች ምስጋናቸውን ያቀርባሉ።
ስለ ኢትዮጵያ ልማት
ኢትዮጵያውያን ግንቦት 24 2018 ዓ.ም ውሳኔያቸውን ሲያስቀምጡ፤ ሀገራቸውን በፍጹም የዲሞክራሲ ባህል ውስጥ ለማንበር ነው። በሌላ በኩል ኢትዮጵያ ባላት ጸጋ ልክ የሚያስፈልጋትን ሁለንተናዊ ልማት በፍጥነት እውን የማድረግ ባህል እንዲቀጥል ሕዝባችን ተናግሯል።
ባለፉት ዓመታት የታየው እውነት እንደሚያሳየን የኢ.ፌ.ዲ.ሪ መንግሥት የተስፋ ቃል መንግሥት አልነበረም፤ ይልቁንም በተጨባጭ የሚታዩ ውጤቶች የተመዘገቡበት ውጤት ተኮር መንግሥት ሲሆን፤ እነዚህም ውጤቶች በግልጽ የሚታዩ ናቸው።
የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ በ2017 በጀት ዓመት የ9.2 በመቶ ዕድገት ያስመዘገበ ሲሆን፤ ይህም በዓለም ላይ ፈጣን ዕድገት ካስመዘገቡ ኢኮኖሚዎች አንዱ ያደርገዋል። ዕድገቱ መነቃቃትን መሠረት በማድረግ በ2018 በጀት ዓመት የኢኮኖሚ ዕድገቱ 10.2 በመቶ ይደርሳል ተብሎ ይጠበቃል። ዕድገቱ ግብርናን፣ ኢንዱስትሪንና የአገልግሎት ዘርፎችን በከፍተኛ ደረጃ ያካተተ ሰፊ መሠረት ያለው ቢሆንም፤ ከጊዜ ወደ ጊዜ ግን ኢንዱስትሪው ለዕድገቱ ዋነኛ አንቀሳቃሽ ኃይል ሆኖ እየመጣ ይገኛል። ይህም መንግሥት ለማኑፋክቸሪንግ፣ ለኢንዱስትሪ ልማት፣ ለዕሴት ጭማሪና ለውጭ ገበያ ተኮር ምርቶች የሰጠውን ቀጣይነት ያለው ትኩረት ያሳያል።
እነዚህ ውጤቶች እንዲሁ ግምቶች ብቻ ሳይሆኑ፤ በጠቅላይ ሚኒስትሩ የ100 ቀናት የሥራ አፈጻጸም ግምገማ ሥርዓት አማካኝነት ክትትል የሚደረግባቸው የተጠያቂነትና የታቀደ አመራር ፍሬዎች ናቸው። አጠቃላይ የወጪ ንግድ ገቢ 20 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር ይደርሳል ተብሎ የሚጠበቅ ሲሆን፤ ይህም ከ2016 ዓ.ም. ወዲህ የ100 በመቶ ገደማ ጭማሪ አሳይቷል።
የዋጋ ግሽበትም ወደ ታች ማሽቆልቆሉን በመቀጠል አሁን ላይ ወደ አንድ አሐዝ ደረጃ እየተቃረበ ይገኛል፤ ይህም በቅርብ ዓመታት ውስጥ በቤተሰቦችና በንግዶች ላይ ከባድ ጫና ፈጥሮ ከነበረው ባለ ሁለት አሐዝ የዋጋ ግሽበት አንጻር ትልቅ መሻሻል ነው። ይህ ስኬት የተመዘገበው ዓለም አቀፍ የኃይል አቅርቦትና ሌሎች ስትራቴጂካዊ ቁሳቁሶችን ገበያ ያናጋው የመካከለኛው ምስራቅ ወቅታዊ ጂኦፖለቲካዊ ውጥረት ጨምሮ፤ ውጫዊ ጫናዎች በነበሩበት ወቅት ነው።
የሀገር በቀል ኢኮኖሚ ማሻሻያ አጀንዳ ከተጀመረ ወዲህ መንግሥት ከውጭ ምንጮች ምንም ዓይነት አዲስ የንግድ ብድር ስምምነት ያላደረገ ሲሆን፤ ይህም የሀገሪቱን የብድር ዕዳ ጫና በከፍተኛ ሁኔታ አቅልሎታል። ከእነዚህ ቁጥሮች በስተጀርባ ኢትዮጵያውያን በዓይናቸው የሚያዩትና በእጃቸው የሚዳስሱት ተጨባጭ ለውጥ አለ። ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ለመኖሪያ ቤቶች፣ ለንግድ ተቋማትና ለጎረቤት ሀገራት የኤሌክትሪክ ኃይል እያመነጨ ይገኛል። ይህ ግድብ በራሳቸው በኢትዮጵያውያን የተደገፈ፣ በኢትዮጵያውያን መሐንዲሶች የተገነባ እና ቀጣይነት የነበረውን ውጫዊ
ጫናዎችን ተቋቁሞ የተጠናቀቀ ነው። ከሃይድሮ ፓወር ጎን ለጎን፤ በኢትዮጵያ ሶማሌ ክልል የሚገኘውን የአይሻ ሁለት የንፋስ ኃይል ማመንጫ እና በአርሲ ዞን የሚገኘውን የአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች፤ በመሳሰሉ ሥራዎች ታዳሽ ኃይል አቅርቦቷን እያሰፋች ሲሆን፤ ይህም የቀጣናዊ ኢነርጂ ትብብርን እያሳደገ የብሔራዊ ኃይል አቅርቦት መረቡን የመቋቋም ዐቅም ያጠናክራል። በአፍሪካ አህጉር ታሪክ ውስጥ ትልቁ የመሠረተ ልማት ኢንቨስትመንት አንዱ የሆነው የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ፕሮጀክት የመሠረት ድንጋይ ተጥሎ ግንባታው ተጀምሯል። እነዚህ ምኞቶች አይደሉም፤ ተጨባጭ ሐቆች ናቸው።
ግብርና፣ አምራች ኢንዱስትሪና ቴክኖሎጂ
በግብርናው ዘርፍ፤ የመንግሥት የምግብ ሉዓላዊነት አጀንዳ ወቅታዊ ለውጦችን ሳይሆን መዋቅራዊ ውጤቶችን እያስገኘ ቀጥሏል። በሶማሌ ክልል የጎዴ ዩሪያ ማዳበሪያ ፋብሪካን ለመገንባት ከአሊኮ ዳንጎቴ ግሩፕ ጋር የተፈረመው አጋርነት የዘመኑ ጉልህ የኢንዱስትሪ ኢንቨስትመንቶች አንዱ ማረጋገጫ ነው። ፋብሪካው በዓመት 3 ሚሊዮን ሜትሪክ ቶን ዩሪያ የማምረት አቅም እንዲኖረው ታቅዶ እየተገነባ ሲሆን፤ ይህም ኢትዮጵያን በዓለም ትላልቅ ማዳበሪያ አምራች ሀገራት ተርታ ያሰልፋታል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ግንቦት 9 ቀን 2018 ዓ.ም. የፕሮጀክቱን የግንባታ ሂደት በጎበኙበት ወቅት እንደገለጹት፤ “ይህ ፕሮጀክት በግብርና ትራንስፎርሜሽን፣ በምግብ ዋስትና፣ በኢንዱስትሪ ዕድገትና በኢኮኖሚ ራስን መቻል ላይ የተደረገ ስትራቴጂካዊ ኢንቨስትመንት ነው” ብለዋል። አስተማማኝ ባልሆነና ውድ በሆነ የማዳበሪያ አቅርቦት ለረጅም ጊዜ ለተገደቡት ኢትዮጵያውያን አምራቾች የዚህ ፕሮጀክት ፋይዳ ፈጣንና ተጨባጭ ነው።
ከዚህ ምርጫ ጥቂት ቀናት ቀደም ብሎ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ግንቦት 19 ቀን 2018 ዓ.ም. በነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ ምርቃት ላይ ሲገኑ የታየው ተምሳሌትነት ለቦረና ሕዝብ ትልቅ ትርጉም ነበረው። ይህ ዞን በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቅበት ስም የሀገርን አንገት ያስደፋ እንደነበር የቅርብ ጊዜ ትውስታ ሲሆን፤ እርሱም ድርቅ ነው።
ለሦስት ተከታታይ ዓመታት የዝናብ መጥፋት በሚሊዮን የሚቆጠሩ ከብቶችን የገደለ፣ ቤተሰቦች ለውኃ ፍለጋ በመቶዎች የሚቆጠሩ ኪሎ ሜትሮችን እንዲጓዙ ያስገደደ፣ እንዲሁም በእነዚህ የግጦሽ መሬቶች ላይ ለዘመናት ራሳቸውን ችለው የኖሩ ማኅበረሰቦችን ለአስቸኳይ የምግብ እርዳታ እጅ እንዲዘረጉ አድርጎ ነበር። ዓለም የሚያውቃት ቦረና እርሷ ነበረች።
የጠቅላይ ሚኒስትሩ የግንቦት ወር ጉብኝት ግን የተለየ ታሪክ አሳይቷል።
አሁን ላይ ለአርብቶ አደር ማኅበረሰቦችና ለከብቶቻቸው ንጹሕ ውኃ እያቀረቡ ያሉትን የውኃና የመስኖ መሠረተ ልማቶችን የገመገሙ ሲሆን፤ ከጥቂት ዓመታት በፊት አቧራ ብቻ በነበረው መሬት ላይ የክላስተር እርሻዎችን ጎብኝተዋል፤ በያቤሎ የባህል ማዕከል መርቀዋል፤ እንዲሁም በአየር ንብረት ሁኔታዎች ምክንያት ቀድሞ ተገልሎ ለነበረው ቀጣና ዓመቱን ሙሉ ትስስር የሚፈጥር አውሮፕላን ማረፊያ መርቀው ከፍተዋል።
የአምራች ዘርፉም ተመሳሳይ የለውጥ ታሪክ አለው። በግንቦት 2018 ዓ.ም. በተካሄደው 4ኛው ኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ ላይ፤ መንግሥት ለአራት ዓመታት የተመዘገበውን ቀጣይነት ያለው የኢንዱስትሪ መስፋፋት ውጤቶች አቅርቧል። የአምራች ዘርፉ የግብአት አቅርቦት በዓመት 9 ሚሊዮን ቶን ወደ 15 ሚሊዮን ቶን አድጓል። የምርት አቅም አጠቃቀም ከ47 በመቶ ወደ 67 በመቶ ከፍ ማለቱን፣ የማኑፋክቸሪንግ ዕድገት ከ4.8 በመቶ ወደ 10.7 በመቶ ማደጉን፣ እንዲሁም ለአነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች የሚቀርበው ፋይናንስ ከ8.1 ቢሊዮን ብር ወደ 50 ቢሊዮን ብር ማደጉን ያሳያል።
እነዚህ ስኬቶች በሀገር ውስጥ ምርት ላይ በከፍተኛ ሁኔታ እየተንጸባረቁ ይገኛሉ። ኤክስፖው በተጠናቀቀ በሃያ ቀናት ውስጥ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዘጠኝ ወራት ውስጥ ብቻ ተጠናቆ ከ80 በመቶ በላይ ጥሬ ዕቃውን ከሀገር ውስጥ የሚያገኘውን ግዙፍ የኢንዱስትሪ ኢንቨስትመንት «ግራንዲዩር የሴራሚክ ማኑፋክቸሪንግ» ፋብሪካን በሞጆ ከተማ መርቀዋል። ቀደም ሲል በገቢ የሴራሚክ ምርቶች ላይ ጥገኛ የነበረችው ኢትዮጵያ አሁን ላይ የሴራሚክ ምርቶችን ከውጭ ማስገባት ሙሉ በሙሉ ለማቆምና ለውጭ ገበያ የሚሆን ምርት ለማስፋፋት እየተዘጋጀች ትገኛለች።
በቴክኖሎጂው ዘርፍም፤ ዘመናዊ ልማት ከጊዜ ወደ ጊዜ በዳታ፣ በፈጠራና በዲጂታል ሥርዓቶች የሚወሰን መሆኑን በመገንዘብ፤ መንግሥት ኢትዮጵያን ሰው ሠራሽ አስተውሎት እና የኢንዱስትሪ 5.0 ማሕቀፎችን ቀድመው ከተገበሩ ሀገራት ተርታ እያሰለፋት ይገኛል።
የጽንፈኝነትን ፖለቲካ ውድቅ ማድረግ
በኦነግ ሸኔ ዐማጽያን በንጹሐን ዜጎች ላይ በተለይም በሃይማኖት ተቋማት ውስጥ ዒላማ ተደርገው የተፈጸሙ ጥቃቶችን ተከተሎ፤ የቤተሰብ እና የወዳጆቻቸውን ሕይወት ላጡ፣ የአካል ጉዳት ለደረሰባቸው እና የቤት ንብረታቸው ለወደመባቸው በአርሲ ዞን ለሚገኙ ወገኖቻችን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በኢትዮጵያ መንግሥት ስም የተሰማቸውን ጥልቅ ኀዘን ይገልጻሉ።
እነዚህ ጥቃቶች የሀገሪቱን ብሔራዊ ዕድገት ለማደናቀፍ ከሚሹ አካላት፣ በአማራ ክልል ከሚንቀሳቀሱ የሀገር ውስጥ አማፂ ቡድኖች እና ለሀገሪቱ ሁለንተናዊ ዕድገት ጥላቻ ካላቸው የውጭ ኃይሎች ጋር በጥምረት የተከናወኑ ሲሆኑ፤ ዓላማቸውም በኢትዮጵያ አለመረጋጋትንና የምርጫ መስተጓጎልን ለመፍጠር ሲደረግ የነበረ የጥፋት ውጥን ተከታይ ነው።
መንግሥት 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ያለ አንዳች የፀጥታ ችግር ፍትሐዊና አሳታፊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ከአንድ ዓመት በላይ የዘለቀ ልዩ ትኩረትና ዝግጅት በማድረግ በቁርጠኝነት ሲሠራ ቆይቷል። በሌላ በኩል የጥፋት ኃይሎች ከባዕዳን ጋር 'ፅምዶ' የሚል ቁርኝት በመፍጠር ዕኩይ ዓላማቸውን ለማሳካት ሰፊ የጥፋት ዝግጅት ሲያደርጉ ቆይተዋል፣ ሀገራዊ ምርጫው እንዳይከናወን ሰፊ ርብርብ አድርገዋል። በተጨባጭም በቅድመ ምርጫ እና በምርጫ ወቅት የዜጎችን የመምረጥ መብትና ነጻነት ለመጋፋትና ለማደናቀፍ አለን የሚሉትን የጥፋት እጅ ዘርግተዋል።
እነዚህ የጠላት ኃይሎች በመደጋገፍና በመናበብ ዐመፅና ሁከት ለማነሳሳት፣ ከተሞችን በሽብር ጥቃት ለማወክ፣ በመንገዶች የደፈጣ ጥቃት በመፈጸም እንቅስቃሴ ለመገደብ እና በተወሰኑ አካባቢዎች ዒላማ አድርገው ነጥሎ ለማጥቃት ተንቀሳቅሰዋል። እንደ ማሳያ የጦር መሣሪያ፣ ተተኳሾችንና ሌሎች ሎጀስቲክሶችን በድጋፍ በማቅረብ በደቡባዊ ትግራይ በሚገኙ አዋሳኝ የአማራ ክልል አንዳንድ ቦታዎች ላይ ትንኮሳ ፈጽመዋል፣ በአማራ ክልል ባሕር ዳር፣ ጎንደር፣ ደብረ ብርሃን እና ወልድያ ከተሞችን ጨምሮ በክልሉ ዋና ዋና ከተሞች እና ሲቪሎች ላይ ዒላማ በማድረግ ያካሄደው የሽብር እንቅስቃሴና ዝግጅት፣ በአዲስ አበባ ከተማ ባደራጃቸው የኅቡዕ ሴሎች አማካኝነት በተመረጡ አከባቢዎች ላይ ጥቃት እንዲፈጸም ተንቀሳቅሰው የነበረ ቢሆንም ይሄን የጥፋት ሴራ እና ድርጊት እንዲከሽፍ ማድረግ ተችሏል።
በተመሳሳይ በኦሮሚያ ክልል የሸኔ ሽብር ቡድን ከጽንፈኛው ፋኖ ታጣቂ ቡድን ጋር በመናበብ በአንዳንድ አካባቢዎች መንገዶችን በመዝጋት እንቅስቃሴ ለማስቆምና ለማስተጓጎል ፍላጎት የተንቀሳቀሰ ቢሆንም በጸጥታ ኃይሉ በተወሰደበት የተጠናከረ እርምጃ ፍላጎቱን ማሳካት አልቻለም። ቡድኑ በፀጥታ ኃይሉ የተወሰደበትን ርምጃ መቋቋም ባለመቻሉ እና ፍላጎቱን ማሳካት ባለመቻሉ ስስ ዒላማዎች ላይ ያተኮረ ርምጃ በመውሰድ የሃይማኖት እና የብሔር ግጭት ለመቀስቀስ በማለም በአርሲ ዞን አሰኮ እና አካባቢው ጥቃት በመፈጸም ሁሉን አይነት የጥፋት ርብርብ ያደረገ ቢሆንም ሁኔታውን በመቆጣጠር ፀጥታ ኃይላችን በእነዚህ ኃይሎች ላይ የተቀናጀ ርምጃ እየወሰደ ይገኛል።
መንግሥት መሰል ሥጋቶችን በንቃት በመከታተል ላይ ሲሆን፣ በምርጫው ወቅትም በብዙ የሀገሪቱ አካባቢዎች የተቀነባበሩ ተመሳሳይ ዕቅዶችን በስኬት ማክሸፍ ችሏል። በንጹሐን ዜጎች ላይ የሚፈጸሙ ጥቃቶችን፤ ፍርሃትና ክፍፍልን ከሚያጎሉ የሚዲያ ዘመቻዎች ጋር በማስተሣሠር የተቀነባበረው ይህ እኩይ ተግባር፤ በመንግሥት የደኅንነት መዋቅርና ኦፕሬሽኖች አማካኝነት በከፍተኛ ሁኔታ እንዲስተጓጎል ተደርጓል። ብሔራዊ እና ሃይማኖታዊ ክፍፍልን ለመዝራት የኃይል ጥቃትን እና ውድመትን እንደ መሣሪያ የሚጠቀሙ አካላት በሁሉም ኢትዮጵያውያን ዘንድ በግልጽ ሊወገዙ ይገባል። መሰል ተግባሮች በኢትዮጵያ ውስጥ ምንም ዓይነት የወደፊት ዕድል እንደሌላቸው ለማሳየት የተቀናጀ ብሔራዊ ምላሽ በመስጠት ወሳኝ ርምጃዎችን ይቀጥላል።
በንጹሐን ዜጎች ላይ ጥቃት የሚፈጸሙ አካላት፣ ድርጊታቸውን ምክንያታዊ ለማስመሰል ምንም ዓይነት የፖለቲካ ንግግር ቢጠቀሙ፤ ወሳኝ ዓላማን እያሳኩ ሳይሆን ወንጀል እየፈጸሙ ነው። የፖለቲካ ቅሬታዎች በኢትዮጵያ ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓት፣ በብሔራዊ ምክክር ሂደት እና በዴሞክራሲያዊ ተቋማት አማካኝነት መፍትሔ ሊያገኙ የሚችሉ እና ሊያገኙ የሚገባቸው ናቸው።
ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም::
የጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት
የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ
የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት
Federal Democratic Republic of Ethiopia
OFFICE OF THE PRIME MINISTER
ጋዜጣዊ መግለጫ
ግንቦት 28 ቀን 2018 ዓ.ም
አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ
ወቅታዊ ጉዳዮችን አስመልክቶ የተሰጠ መግለጫ
#ethiopia | ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. ማለዳ ላይ፤ የመጀመሪያው የወገግታ ጭላንጭል በከፍታማዎቹ የኢትዮጵያ ተራሮች ላይ ፈንጥቆ ጨለማውን ሳይቀድ በፊት ኢትዮጵያውያን ረጃጅም ሰልፍ ተሰልፈዋል። በጅማ፣ በድሬዳዋ፣ በሐዋሳ፣ በባሕር ዳር እንዲሁም ስማቸው በዓለም አቀፍ የዜና ጋዜጣዎች ላይ ፈጽሞ ሊወጣ በማይችሉ ከተሞችና መንደሮች ውስጥ ያሉ ወንዶችና ሴቶች፤ ወሳኝ ተግባር ለመፈጸም በሰልፍ ቆሙ። ድምፅ ሰጡ! ይህንን ታሪካዊ ኃላፊነት ለመወጣት ከሃምሳ አራት ሚልዮን በላይ የሚሆኑ ዜጎች ተመዝግበው ነበር። ይህ ቁጥር ከአንዳንድ ሀገሮች አጠቃላይ ሕዝብ ቁጥር በላይ ነው። ይህ ምርጫ እውነተኛ ስለመሆኑ ጥያቄ ለሚያነሣ ለማንኛውም አካል ግልጽ እና የማያሻማ ምላሽ ሰጥቷል!
የኢትዮጵያ ሕዝብ ፍላጎት
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከ52,000 ምርጫ ጣቢያዎች መካከል ከ50,188 በላይ የሚሆኑት በሰዓቱ ተከፍተው ቀኑን ሙሉ መራጮችን ሲያስተናግዱ እንደነበር አረጋግጧል። ከ42 የፖለቲካ ፓርቲዎች የተወጣጡ ከ10,438 በላይ ዕጩዎች እና 80 የግል እጩዎች በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እና የክልል ምክር ቤት ወንበሮችን ለማሸነፍ ተወዳድረዋል። ይህ በማንኛውም ሊለካ በሚችል መሥፈርት በኢትዮጵያ ታሪክ ትልቁ እና በውሳኔ አሰጣጥም ሆነ በአስተዳደራዊ ረገድ እጅግ በረቀቀ ሁኔታ ተግባራዊ የተደረገ ዴሞክራሲያዊ ተሳትፎ የታየበት ኩነት ነበር።
የቀድሞው የኬንያ ፕሬዚዳንት ክቡር ኡሁሩ ኬንያታ የሚመሩትና ከ37 የአፍሪካ ሀገሮች የተወጣጡ 83 ታዛቢዎችን ያቀፈው የአፍሪካ ኅብረት የምርጫ ታዛቢ ቡድን ምርጫውን “ዲሞክራሲያዊ አስተዳደርን በሰፊው በሚደግፍ ሕጋዊና ተቋማዊ ማዕቀፍ ውስጥ የተካሄደ” ሲል ገምግሞታል።
በቀድሞዋ የኡጋንዳ ምክትል ፕሬዚዳንት ክቡር ዶክተር ስፔሲዮዛ ዋንዲራ ካዚብዌ የሚመራው የኢጋድ የምርጫ ታዛቢ ቡድን ባወጣው የመጀመሪያ ደረጃ ሪፖርት፤ በታዘቡባቸው ጣቢያዎች ሁሉ የምርጫ ሳጥኖች በትክክል የታሸጉ መሆናቸውን፣ የፓርቲ ወኪሎች በሂደቱ በሙሉ መገኘታቸውን እንዲሁም ምርጫው አስደናቂ ተቋማዊ፣ አስተዳደራዊና የቴክኖሎጂ ዕድገትን ያሳየ መሆናቸውን አረጋግጧል። የኢጋድ የምርጫ ታዛቢ ልዑክ ይህንን ምርጫ “የበርካታ አዳዲስ ምዕራፎች ምርጫ” ሲል ሰይሞታል።
የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን በድምፅ መስጠት ሂደት ውስጥ ምንም ዓይነት የሰብዓዊ መብት ጥሰት እንዳልተመለከተ አረጋግጧል። የሲቪክ ማኅበረሰብ ታዛቢዎች ጥምረት በምርጫ ቦርድ ዕውቅና ከተሰጧቸው 55 ድርጅቶች 65,299 ታዛቢዎችን በመላ ሀገሪቱ ያሠማራ ሲሆን፤ 99 በመቶ የምርጫ ጣቢያዎች ላይ ያለምንም ዕንቅፋት የመታዘብ ዕድል ማግኘቱን አረጋግጧል። እነዚህ ተዓማኒነት ያላቸው ሀገራዊ እና አኅጉራዊ ተቋማት ያደረጓቸው ግምገማዎችና የሰጧቸው እውነተኛ ፍርዶች ናቸው። እነዚህ ለአፍሪካ ጥላቻ ካላቸው ወይም የአፍሪካን ዴሞክራሲ በውጫዊ መሥፈርቶች ከሚለኩ ተቋማት የተደመጡ ድምፆች አይደሉም።
አንዳንድ ዓለም አቀፍ ተንታኞች ይህንን ምርጫ እንደ ንግሥና በዓል አድርገው ያቆሸሹት ሲሆን ውጤቱም አስቀድሞ የተወሰነ ድራማ እንደነበር አድርገው ሊያቀርቡት ሞክረዋል። እነዚህን መግለጫዎች ከአውነታው የራቁ፣ በጥናትና ትንተና ላይ ያልተመሠረቱ እንዲሁም ነፃና የታሰበበት ዲሞክራሲያዊ ምርጫቸውን በኩራት ላደረጉ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን ክብር የማይሰጡ በመሆናቸው የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ሙሉ በሙሉ የማይቀበላቸው መሆኑን ያረግጣል። አስቀድሞ የተወሰነ ውጤት ቢኖር ኖሮ፤ ከ37 የአፍሪካ ሀገሮች የተወጣጡ 83 ገለልተኛ ታዛቢዎችን፣ 65,299 የሀገር ውስጥ የሲቪል ማኅበረሰብ ታዛቢዎችን ወይም 1,100 ዕውቅና የተሰጣቸውን የዓለም አቀፍ ጋዜጠኞችን መጋበዝ ባላስፈለገ ነበር።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በዚህ ሀገራዊ ምርጫ ለተሳተፉ የኢትዮጵያ ዜጎች፤ ለብሔራዊ ምርጫ ቦርድ እና ላሠማራቸው ከ350,000 በላይ ኃላፊዎች፤ ሂደቱን ለመጠበቅ የጸጥታ ኃይሎች እንዲሁም ኢትዮጵያ ለዲሞክራሲ ግንባታ መጎልበት እና ለሂደቱ መሳካት ያላትን ቁርጠኝነት ላረጋገጡት የአፍሪካ እና ቀጠናዊ የታዛቢ ቡድኖች ምስጋናቸውን ያቀርባሉ።
ስለ ኢትዮጵያ ልማት
ኢትዮጵያውያን ግንቦት 24 2018 ዓ.ም ውሳኔያቸውን ሲያስቀምጡ፤ ሀገራቸውን በፍጹም የዲሞክራሲ ባህል ውስጥ ለማንበር ነው። በሌላ በኩል ኢትዮጵያ ባላት ጸጋ ልክ የሚያስፈልጋትን ሁለንተናዊ ልማት በፍጥነት እውን የማድረግ ባህል እንዲቀጥል ሕዝባችን ተናግሯል።
ባለፉት ዓመታት የታየው እውነት እንደሚያሳየን የኢ.ፌ.ዲ.ሪ መንግሥት የተስፋ ቃል መንግሥት አልነበረም፤ ይልቁንም በተጨባጭ የሚታዩ ውጤቶች የተመዘገቡበት ውጤት ተኮር መንግሥት ሲሆን፤ እነዚህም ውጤቶች በግልጽ የሚታዩ ናቸው።
የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ በ2017 በጀት ዓመት የ9.2 በመቶ ዕድገት ያስመዘገበ ሲሆን፤ ይህም በዓለም ላይ ፈጣን ዕድገት ካስመዘገቡ ኢኮኖሚዎች አንዱ ያደርገዋል። ዕድገቱ መነቃቃትን መሠረት በማድረግ በ2018 በጀት ዓመት የኢኮኖሚ ዕድገቱ 10.2 በመቶ ይደርሳል ተብሎ ይጠበቃል። ዕድገቱ ግብርናን፣ ኢንዱስትሪንና የአገልግሎት ዘርፎችን በከፍተኛ ደረጃ ያካተተ ሰፊ መሠረት ያለው ቢሆንም፤ ከጊዜ ወደ ጊዜ ግን ኢንዱስትሪው ለዕድገቱ ዋነኛ አንቀሳቃሽ ኃይል ሆኖ እየመጣ ይገኛል። ይህም መንግሥት ለማኑፋክቸሪንግ፣ ለኢንዱስትሪ ልማት፣ ለዕሴት ጭማሪና ለውጭ ገበያ ተኮር ምርቶች የሰጠውን ቀጣይነት ያለው ትኩረት ያሳያል።
እነዚህ ውጤቶች እንዲሁ ግምቶች ብቻ ሳይሆኑ፤ በጠቅላይ ሚኒስትሩ የ100 ቀናት የሥራ አፈጻጸም ግምገማ ሥርዓት አማካኝነት ክትትል የሚደረግባቸው የተጠያቂነትና የታቀደ አመራር ፍሬዎች ናቸው። አጠቃላይ የወጪ ንግድ ገቢ 20 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር ይደርሳል ተብሎ የሚጠበቅ ሲሆን፤ ይህም ከ2016 ዓ.ም. ወዲህ የ100 በመቶ ገደማ ጭማሪ አሳይቷል።
የዋጋ ግሽበትም ወደ ታች ማሽቆልቆሉን በመቀጠል አሁን ላይ ወደ አንድ አሐዝ ደረጃ እየተቃረበ ይገኛል፤ ይህም በቅርብ ዓመታት ውስጥ በቤተሰቦችና በንግዶች ላይ ከባድ ጫና ፈጥሮ ከነበረው ባለ ሁለት አሐዝ የዋጋ ግሽበት አንጻር ትልቅ መሻሻል ነው። ይህ ስኬት የተመዘገበው ዓለም አቀፍ የኃይል አቅርቦትና ሌሎች ስትራቴጂካዊ ቁሳቁሶችን ገበያ ያናጋው የመካከለኛው ምስራቅ ወቅታዊ ጂኦፖለቲካዊ ውጥረት ጨምሮ፤ ውጫዊ ጫናዎች በነበሩበት ወቅት ነው።
የሀገር በቀል ኢኮኖሚ ማሻሻያ አጀንዳ ከተጀመረ ወዲህ መንግሥት ከውጭ ምንጮች ምንም ዓይነት አዲስ የንግድ ብድር ስምምነት ያላደረገ ሲሆን፤ ይህም የሀገሪቱን የብድር ዕዳ ጫና በከፍተኛ ሁኔታ አቅልሎታል። ከእነዚህ ቁጥሮች በስተጀርባ ኢትዮጵያውያን በዓይናቸው የሚያዩትና በእጃቸው የሚዳስሱት ተጨባጭ ለውጥ አለ። ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ለመኖሪያ ቤቶች፣ ለንግድ ተቋማትና ለጎረቤት ሀገራት የኤሌክትሪክ ኃይል እያመነጨ ይገኛል። ይህ ግድብ በራሳቸው በኢትዮጵያውያን የተደገፈ፣ በኢትዮጵያውያን መሐንዲሶች የተገነባ እና ቀጣይነት የነበረውን ውጫዊ
ጫናዎችን ተቋቁሞ የተጠናቀቀ ነው። ከሃይድሮ ፓወር ጎን ለጎን፤ በኢትዮጵያ ሶማሌ ክልል የሚገኘውን የአይሻ ሁለት የንፋስ ኃይል ማመንጫ እና በአርሲ ዞን የሚገኘውን የአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች፤ በመሳሰሉ ሥራዎች ታዳሽ ኃይል አቅርቦቷን እያሰፋች ሲሆን፤ ይህም የቀጣናዊ ኢነርጂ ትብብርን እያሳደገ የብሔራዊ ኃይል አቅርቦት መረቡን የመቋቋም ዐቅም ያጠናክራል። በአፍሪካ አህጉር ታሪክ ውስጥ ትልቁ የመሠረተ ልማት ኢንቨስትመንት አንዱ የሆነው የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ፕሮጀክት የመሠረት ድንጋይ ተጥሎ ግንባታው ተጀምሯል። እነዚህ ምኞቶች አይደሉም፤ ተጨባጭ ሐቆች ናቸው።
ግብርና፣ አምራች ኢንዱስትሪና ቴክኖሎጂ
በግብርናው ዘርፍ፤ የመንግሥት የምግብ ሉዓላዊነት አጀንዳ ወቅታዊ ለውጦችን ሳይሆን መዋቅራዊ ውጤቶችን እያስገኘ ቀጥሏል። በሶማሌ ክልል የጎዴ ዩሪያ ማዳበሪያ ፋብሪካን ለመገንባት ከአሊኮ ዳንጎቴ ግሩፕ ጋር የተፈረመው አጋርነት የዘመኑ ጉልህ የኢንዱስትሪ ኢንቨስትመንቶች አንዱ ማረጋገጫ ነው። ፋብሪካው በዓመት 3 ሚሊዮን ሜትሪክ ቶን ዩሪያ የማምረት አቅም እንዲኖረው ታቅዶ እየተገነባ ሲሆን፤ ይህም ኢትዮጵያን በዓለም ትላልቅ ማዳበሪያ አምራች ሀገራት ተርታ ያሰልፋታል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ግንቦት 9 ቀን 2018 ዓ.ም. የፕሮጀክቱን የግንባታ ሂደት በጎበኙበት ወቅት እንደገለጹት፤ “ይህ ፕሮጀክት በግብርና ትራንስፎርሜሽን፣ በምግብ ዋስትና፣ በኢንዱስትሪ ዕድገትና በኢኮኖሚ ራስን መቻል ላይ የተደረገ ስትራቴጂካዊ ኢንቨስትመንት ነው” ብለዋል። አስተማማኝ ባልሆነና ውድ በሆነ የማዳበሪያ አቅርቦት ለረጅም ጊዜ ለተገደቡት ኢትዮጵያውያን አምራቾች የዚህ ፕሮጀክት ፋይዳ ፈጣንና ተጨባጭ ነው።
ከዚህ ምርጫ ጥቂት ቀናት ቀደም ብሎ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ግንቦት 19 ቀን 2018 ዓ.ም. በነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ ምርቃት ላይ ሲገኑ የታየው ተምሳሌትነት ለቦረና ሕዝብ ትልቅ ትርጉም ነበረው። ይህ ዞን በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቅበት ስም የሀገርን አንገት ያስደፋ እንደነበር የቅርብ ጊዜ ትውስታ ሲሆን፤ እርሱም ድርቅ ነው።
ለሦስት ተከታታይ ዓመታት የዝናብ መጥፋት በሚሊዮን የሚቆጠሩ ከብቶችን የገደለ፣ ቤተሰቦች ለውኃ ፍለጋ በመቶዎች የሚቆጠሩ ኪሎ ሜትሮችን እንዲጓዙ ያስገደደ፣ እንዲሁም በእነዚህ የግጦሽ መሬቶች ላይ ለዘመናት ራሳቸውን ችለው የኖሩ ማኅበረሰቦችን ለአስቸኳይ የምግብ እርዳታ እጅ እንዲዘረጉ አድርጎ ነበር። ዓለም የሚያውቃት ቦረና እርሷ ነበረች።
የጠቅላይ ሚኒስትሩ የግንቦት ወር ጉብኝት ግን የተለየ ታሪክ አሳይቷል።
አሁን ላይ ለአርብቶ አደር ማኅበረሰቦችና ለከብቶቻቸው ንጹሕ ውኃ እያቀረቡ ያሉትን የውኃና የመስኖ መሠረተ ልማቶችን የገመገሙ ሲሆን፤ ከጥቂት ዓመታት በፊት አቧራ ብቻ በነበረው መሬት ላይ የክላስተር እርሻዎችን ጎብኝተዋል፤ በያቤሎ የባህል ማዕከል መርቀዋል፤ እንዲሁም በአየር ንብረት ሁኔታዎች ምክንያት ቀድሞ ተገልሎ ለነበረው ቀጣና ዓመቱን ሙሉ ትስስር የሚፈጥር አውሮፕላን ማረፊያ መርቀው ከፍተዋል።
የአምራች ዘርፉም ተመሳሳይ የለውጥ ታሪክ አለው። በግንቦት 2018 ዓ.ም. በተካሄደው 4ኛው ኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ ላይ፤ መንግሥት ለአራት ዓመታት የተመዘገበውን ቀጣይነት ያለው የኢንዱስትሪ መስፋፋት ውጤቶች አቅርቧል። የአምራች ዘርፉ የግብአት አቅርቦት በዓመት 9 ሚሊዮን ቶን ወደ 15 ሚሊዮን ቶን አድጓል። የምርት አቅም አጠቃቀም ከ47 በመቶ ወደ 67 በመቶ ከፍ ማለቱን፣ የማኑፋክቸሪንግ ዕድገት ከ4.8 በመቶ ወደ 10.7 በመቶ ማደጉን፣ እንዲሁም ለአነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች የሚቀርበው ፋይናንስ ከ8.1 ቢሊዮን ብር ወደ 50 ቢሊዮን ብር ማደጉን ያሳያል።
እነዚህ ስኬቶች በሀገር ውስጥ ምርት ላይ በከፍተኛ ሁኔታ እየተንጸባረቁ ይገኛሉ። ኤክስፖው በተጠናቀቀ በሃያ ቀናት ውስጥ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዘጠኝ ወራት ውስጥ ብቻ ተጠናቆ ከ80 በመቶ በላይ ጥሬ ዕቃውን ከሀገር ውስጥ የሚያገኘውን ግዙፍ የኢንዱስትሪ ኢንቨስትመንት «ግራንዲዩር የሴራሚክ ማኑፋክቸሪንግ» ፋብሪካን በሞጆ ከተማ መርቀዋል። ቀደም ሲል በገቢ የሴራሚክ ምርቶች ላይ ጥገኛ የነበረችው ኢትዮጵያ አሁን ላይ የሴራሚክ ምርቶችን ከውጭ ማስገባት ሙሉ በሙሉ ለማቆምና ለውጭ ገበያ የሚሆን ምርት ለማስፋፋት እየተዘጋጀች ትገኛለች።
በቴክኖሎጂው ዘርፍም፤ ዘመናዊ ልማት ከጊዜ ወደ ጊዜ በዳታ፣ በፈጠራና በዲጂታል ሥርዓቶች የሚወሰን መሆኑን በመገንዘብ፤ መንግሥት ኢትዮጵያን ሰው ሠራሽ አስተውሎት እና የኢንዱስትሪ 5.0 ማሕቀፎችን ቀድመው ከተገበሩ ሀገራት ተርታ እያሰለፋት ይገኛል።
የጽንፈኝነትን ፖለቲካ ውድቅ ማድረግ
በኦነግ ሸኔ ዐማጽያን በንጹሐን ዜጎች ላይ በተለይም በሃይማኖት ተቋማት ውስጥ ዒላማ ተደርገው የተፈጸሙ ጥቃቶችን ተከተሎ፤ የቤተሰብ እና የወዳጆቻቸውን ሕይወት ላጡ፣ የአካል ጉዳት ለደረሰባቸው እና የቤት ንብረታቸው ለወደመባቸው በአርሲ ዞን ለሚገኙ ወገኖቻችን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በኢትዮጵያ መንግሥት ስም የተሰማቸውን ጥልቅ ኀዘን ይገልጻሉ።
እነዚህ ጥቃቶች የሀገሪቱን ብሔራዊ ዕድገት ለማደናቀፍ ከሚሹ አካላት፣ በአማራ ክልል ከሚንቀሳቀሱ የሀገር ውስጥ አማፂ ቡድኖች እና ለሀገሪቱ ሁለንተናዊ ዕድገት ጥላቻ ካላቸው የውጭ ኃይሎች ጋር በጥምረት የተከናወኑ ሲሆኑ፤ ዓላማቸውም በኢትዮጵያ አለመረጋጋትንና የምርጫ መስተጓጎልን ለመፍጠር ሲደረግ የነበረ የጥፋት ውጥን ተከታይ ነው።
መንግሥት 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ያለ አንዳች የፀጥታ ችግር ፍትሐዊና አሳታፊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ከአንድ ዓመት በላይ የዘለቀ ልዩ ትኩረትና ዝግጅት በማድረግ በቁርጠኝነት ሲሠራ ቆይቷል። በሌላ በኩል የጥፋት ኃይሎች ከባዕዳን ጋር 'ፅምዶ' የሚል ቁርኝት በመፍጠር ዕኩይ ዓላማቸውን ለማሳካት ሰፊ የጥፋት ዝግጅት ሲያደርጉ ቆይተዋል፣ ሀገራዊ ምርጫው እንዳይከናወን ሰፊ ርብርብ አድርገዋል። በተጨባጭም በቅድመ ምርጫ እና በምርጫ ወቅት የዜጎችን የመምረጥ መብትና ነጻነት ለመጋፋትና ለማደናቀፍ አለን የሚሉትን የጥፋት እጅ ዘርግተዋል።
እነዚህ የጠላት ኃይሎች በመደጋገፍና በመናበብ ዐመፅና ሁከት ለማነሳሳት፣ ከተሞችን በሽብር ጥቃት ለማወክ፣ በመንገዶች የደፈጣ ጥቃት በመፈጸም እንቅስቃሴ ለመገደብ እና በተወሰኑ አካባቢዎች ዒላማ አድርገው ነጥሎ ለማጥቃት ተንቀሳቅሰዋል። እንደ ማሳያ የጦር መሣሪያ፣ ተተኳሾችንና ሌሎች ሎጀስቲክሶችን በድጋፍ በማቅረብ በደቡባዊ ትግራይ በሚገኙ አዋሳኝ የአማራ ክልል አንዳንድ ቦታዎች ላይ ትንኮሳ ፈጽመዋል፣ በአማራ ክልል ባሕር ዳር፣ ጎንደር፣ ደብረ ብርሃን እና ወልድያ ከተሞችን ጨምሮ በክልሉ ዋና ዋና ከተሞች እና ሲቪሎች ላይ ዒላማ በማድረግ ያካሄደው የሽብር እንቅስቃሴና ዝግጅት፣ በአዲስ አበባ ከተማ ባደራጃቸው የኅቡዕ ሴሎች አማካኝነት በተመረጡ አከባቢዎች ላይ ጥቃት እንዲፈጸም ተንቀሳቅሰው የነበረ ቢሆንም ይሄን የጥፋት ሴራ እና ድርጊት እንዲከሽፍ ማድረግ ተችሏል።
በተመሳሳይ በኦሮሚያ ክልል የሸኔ ሽብር ቡድን ከጽንፈኛው ፋኖ ታጣቂ ቡድን ጋር በመናበብ በአንዳንድ አካባቢዎች መንገዶችን በመዝጋት እንቅስቃሴ ለማስቆምና ለማስተጓጎል ፍላጎት የተንቀሳቀሰ ቢሆንም በጸጥታ ኃይሉ በተወሰደበት የተጠናከረ እርምጃ ፍላጎቱን ማሳካት አልቻለም። ቡድኑ በፀጥታ ኃይሉ የተወሰደበትን ርምጃ መቋቋም ባለመቻሉ እና ፍላጎቱን ማሳካት ባለመቻሉ ስስ ዒላማዎች ላይ ያተኮረ ርምጃ በመውሰድ የሃይማኖት እና የብሔር ግጭት ለመቀስቀስ በማለም በአርሲ ዞን አሰኮ እና አካባቢው ጥቃት በመፈጸም ሁሉን አይነት የጥፋት ርብርብ ያደረገ ቢሆንም ሁኔታውን በመቆጣጠር ፀጥታ ኃይላችን በእነዚህ ኃይሎች ላይ የተቀናጀ ርምጃ እየወሰደ ይገኛል።
መንግሥት መሰል ሥጋቶችን በንቃት በመከታተል ላይ ሲሆን፣ በምርጫው ወቅትም በብዙ የሀገሪቱ አካባቢዎች የተቀነባበሩ ተመሳሳይ ዕቅዶችን በስኬት ማክሸፍ ችሏል። በንጹሐን ዜጎች ላይ የሚፈጸሙ ጥቃቶችን፤ ፍርሃትና ክፍፍልን ከሚያጎሉ የሚዲያ ዘመቻዎች ጋር በማስተሣሠር የተቀነባበረው ይህ እኩይ ተግባር፤ በመንግሥት የደኅንነት መዋቅርና ኦፕሬሽኖች አማካኝነት በከፍተኛ ሁኔታ እንዲስተጓጎል ተደርጓል። ብሔራዊ እና ሃይማኖታዊ ክፍፍልን ለመዝራት የኃይል ጥቃትን እና ውድመትን እንደ መሣሪያ የሚጠቀሙ አካላት በሁሉም ኢትዮጵያውያን ዘንድ በግልጽ ሊወገዙ ይገባል። መሰል ተግባሮች በኢትዮጵያ ውስጥ ምንም ዓይነት የወደፊት ዕድል እንደሌላቸው ለማሳየት የተቀናጀ ብሔራዊ ምላሽ በመስጠት ወሳኝ ርምጃዎችን ይቀጥላል።
በንጹሐን ዜጎች ላይ ጥቃት የሚፈጸሙ አካላት፣ ድርጊታቸውን ምክንያታዊ ለማስመሰል ምንም ዓይነት የፖለቲካ ንግግር ቢጠቀሙ፤ ወሳኝ ዓላማን እያሳኩ ሳይሆን ወንጀል እየፈጸሙ ነው። የፖለቲካ ቅሬታዎች በኢትዮጵያ ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓት፣ በብሔራዊ ምክክር ሂደት እና በዴሞክራሲያዊ ተቋማት አማካኝነት መፍትሔ ሊያገኙ የሚችሉ እና ሊያገኙ የሚገባቸው ናቸው።
ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም::
የጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት
1 day ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም የተካሄደውን 7ኛውን አጠቃላይ ምርጫ የታዘቡት የአፍሪካ ኅብረት እና የምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት ባለሥልጣን (ኢጋድ) የምርጫ ታዛቢ ልዑካን ቡድኖች የመጀመሪያ ደረጃ ግኝቶቻቸውን በአዲስ አበባ በጋራ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ይፋ አድርገዋል። ሁለቱም ተቋማት በሀገሪቱ ዘላቂ ሰላምና ብሔራዊ መግባባት ለመፍጠር እንዲሁም እምነትን ለማጎልበት አካቶ አጠቃላይ እና ቀጣይነት ያለው የፖለቲካ ውይይት መደረግ እንዳለበት ጥሪ አቅርበዋል።
በቀድሞው የኬንያ ፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬንያታ የሚመራው የአፍሪካ ኅብረት የምርጫ ታዛቢ ቡድን ባወጣው መግለጫ፣ በፖለቲካ ኃይሎች መካከል ልዩነቶችን ለመፍታት እና ዲሞክራሲያዊ አስተዳደርን ለማጠናከር ውይይት ወሳኝ መሆኑን ገልጿል። ይህ ውይይት በሀገሪቱ ሕገ-መንግሥታዊ ማዕቀፍ ውስጥ ልዩነቶችን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት እና የዜጎችን ተሳትፎ ለማሳደግ መርዳት እንዳለበት ቡድኑ ጠቁሟል። በተጨማሪም የፖለቲካ ብዙሃነትን ማሳደግ እና ዜጎች መብቶቻቸውን በነፃነት የሚለማመዱበት ምቹ ሁኔታ መፍጠር እንደሚያስፈልግ አሳስቧል።
በጋዜጣዊ መግለጫው ላይ በትግራይ እና ምርጫ ባልተካሄደባቸው ሌሎች አካባቢዎች ላይ ቡድኑ ለምን ምክረ-ሐሳብ አላካተተም ተብሎ ለቀረበለት ጥያቄ፣ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የጸጥታ ሁኔታው ሲሻሻል ምርጫውን ለማካሄድ ዝግጁ መሆኑን እንዳረጋገጠላቸው ኬንያታ ምላሽ ሰጥተዋል። ታዛቢ ቡድኑ ይህንን ያልተጠናቀቀ የምርጫ ሂደት በቀጣይ እንደሚከታተልም ገልጿል።
በሌላ በኩል በምርጫው ወቅት የአንዳንድ መገናኛ ብዙሃን ፈቃድ መታገድን እና የሚዲያ ነፃነትን በተመለከተ ለቀረበው ጥያቄ ታዛቢ ቡድኑ ቀጥተኛ ምላሽ ከመስጠት የተቆጠበ ሲሆን፣ ዝርዝር ምልከታው በመጨረሻው ሪፖርት ላይ እንደሚወጣ አስታውቋል። ገዥው የብልጽግና ፓርቲ በምርጫ ሊሸነፍ የሚችልበት እውነተኛ ዕድል ስለመኖሩ እና ስለ ምርጫው ተወዳዳሪነት ለቀረበው ጥያቄ ኬንያታ ሲመልሱ፣ ምርጫው ተወዳዳሪ እንደነበር በመግለጽ ተሟግተዋል። በዲሞክራሲያዊ ምርጫ ውስጥ መሳተፍ የውጤቱን አለመታወቅ እና የሽንፈትን ዕድል መቀበልን አብሮ የሚያካትት መሆኑን አብራርተዋል። የአፍሪካ ኅብረት ለዚህ ምርጫ ከተለያዩ 37 የአፍሪካ ሀገራት የተውጣጡ 73 የአጭር ጊዜ ታዛቢዎችን አሰማርቶ የነበረ ሲሆን፣ በቀጣዮቹ ወራት የተሟላ የመጨረሻ ሪፖርት እንደሚያወጣ አስታውቋል።
በቀድሞዋ የኡጋንዳ ምክትል ፕሬዝዳንት ዶክተር ዋንዲራ ስፔሲዮሳ ካዚብዌ የሚመራው የኢጋድ ታዛቢ ቡድን በበኩሉ፣ ምርጫው በኢትዮጵያ ዲሞክራሲያዊ እና ምርጫ ዕድገት ላይ ትልቅ ምዕራፍ መሆኑን ገልጿል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ባስተዋወቃቸው ተቋማዊ እና ቴክኖሎጂያዊ ማሻሻያዎች ምክንያት ውድድሩን የበርካታ አዳዲስ ነገሮች ማሳያ ምርጫ ሲል ጠርቶታል። የኢጋድ ልዑክ 26 ታዛቢዎችን በሰባት ክልሎችና የከተማ አስተዳደሮች አሰማርቶ የነበረ መሆኑም ታውቋል።
በዘንድሮው የኢትዮጵያ 7ኛ አጠቃላይ ምርጫ ከ54 ሚሊዮን በላይ መራጮች የተመዘገቡ ሲሆን፣ ውድድሩ ከ547 የምርጫ ክልሎች ውስጥ በ501ዱ እና በአገር አቀፍ ደረጃ ባሉ 52 ሺህ ገደማ የምርጫ ጣቢያዎች ተካሂዷል።
ይሁን እንጂ በምርጫው ዕለት በጸጥታ ስጋት ምክንያት 143 የምርጫ ጣቢያዎች ሳይከፈቱ ቀርተዋል። በኦሮሚያ እና በአማራ ክልሎች፣ በተለይም እንደ ቢሎኖፓ፣ መቆሳቺ፣ ቀርሳ እና ኩታበር ባሉ አካባቢዎች ድምጽ አሰጣጥ ከተጀመረ በኋላ በጸጥታ እክሎች ምክንያት መቋረጡን ቦርዱ አስታውቋል። በትግራይ ክልል እንዲሁም በአማራና በኦሮሚያ አንዳንድ አካባቢዎች በጸጥታና በሎጅስቲክስ ምክንያት ድምጽ አልተሰጠም። ይህ ከመደረጉ በፊት ተቃዋሚዎችና ታዛቢዎች በእነዚህ አካባቢዎች ያለው ግጭት የመራጮችን ተሳትፎ ሊጎዳ እንደሚችል ስጋታቸውን ገልጸው ነበር። ምንም እንኳን እነዚህ መስተጓጎሎች ቢያጋጥሙም፣ በአብዛኛዎቹ የሀገሪቱ አካባቢዎች ድምጽ አሰጣጡ በሰላማዊ መንገድ የተጠናቀቀ ሲሆን፣ የዚህ ምርጫ የመጨረሻ ውጤት በመጪው ሰኔ 4 ቀን 2018 ዓ.ም ይፋ ይሆናል ተብሎ ይጠበቃል።
በቀድሞው የኬንያ ፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬንያታ የሚመራው የአፍሪካ ኅብረት የምርጫ ታዛቢ ቡድን ባወጣው መግለጫ፣ በፖለቲካ ኃይሎች መካከል ልዩነቶችን ለመፍታት እና ዲሞክራሲያዊ አስተዳደርን ለማጠናከር ውይይት ወሳኝ መሆኑን ገልጿል። ይህ ውይይት በሀገሪቱ ሕገ-መንግሥታዊ ማዕቀፍ ውስጥ ልዩነቶችን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት እና የዜጎችን ተሳትፎ ለማሳደግ መርዳት እንዳለበት ቡድኑ ጠቁሟል። በተጨማሪም የፖለቲካ ብዙሃነትን ማሳደግ እና ዜጎች መብቶቻቸውን በነፃነት የሚለማመዱበት ምቹ ሁኔታ መፍጠር እንደሚያስፈልግ አሳስቧል።
በጋዜጣዊ መግለጫው ላይ በትግራይ እና ምርጫ ባልተካሄደባቸው ሌሎች አካባቢዎች ላይ ቡድኑ ለምን ምክረ-ሐሳብ አላካተተም ተብሎ ለቀረበለት ጥያቄ፣ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የጸጥታ ሁኔታው ሲሻሻል ምርጫውን ለማካሄድ ዝግጁ መሆኑን እንዳረጋገጠላቸው ኬንያታ ምላሽ ሰጥተዋል። ታዛቢ ቡድኑ ይህንን ያልተጠናቀቀ የምርጫ ሂደት በቀጣይ እንደሚከታተልም ገልጿል።
በሌላ በኩል በምርጫው ወቅት የአንዳንድ መገናኛ ብዙሃን ፈቃድ መታገድን እና የሚዲያ ነፃነትን በተመለከተ ለቀረበው ጥያቄ ታዛቢ ቡድኑ ቀጥተኛ ምላሽ ከመስጠት የተቆጠበ ሲሆን፣ ዝርዝር ምልከታው በመጨረሻው ሪፖርት ላይ እንደሚወጣ አስታውቋል። ገዥው የብልጽግና ፓርቲ በምርጫ ሊሸነፍ የሚችልበት እውነተኛ ዕድል ስለመኖሩ እና ስለ ምርጫው ተወዳዳሪነት ለቀረበው ጥያቄ ኬንያታ ሲመልሱ፣ ምርጫው ተወዳዳሪ እንደነበር በመግለጽ ተሟግተዋል። በዲሞክራሲያዊ ምርጫ ውስጥ መሳተፍ የውጤቱን አለመታወቅ እና የሽንፈትን ዕድል መቀበልን አብሮ የሚያካትት መሆኑን አብራርተዋል። የአፍሪካ ኅብረት ለዚህ ምርጫ ከተለያዩ 37 የአፍሪካ ሀገራት የተውጣጡ 73 የአጭር ጊዜ ታዛቢዎችን አሰማርቶ የነበረ ሲሆን፣ በቀጣዮቹ ወራት የተሟላ የመጨረሻ ሪፖርት እንደሚያወጣ አስታውቋል።
በቀድሞዋ የኡጋንዳ ምክትል ፕሬዝዳንት ዶክተር ዋንዲራ ስፔሲዮሳ ካዚብዌ የሚመራው የኢጋድ ታዛቢ ቡድን በበኩሉ፣ ምርጫው በኢትዮጵያ ዲሞክራሲያዊ እና ምርጫ ዕድገት ላይ ትልቅ ምዕራፍ መሆኑን ገልጿል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ባስተዋወቃቸው ተቋማዊ እና ቴክኖሎጂያዊ ማሻሻያዎች ምክንያት ውድድሩን የበርካታ አዳዲስ ነገሮች ማሳያ ምርጫ ሲል ጠርቶታል። የኢጋድ ልዑክ 26 ታዛቢዎችን በሰባት ክልሎችና የከተማ አስተዳደሮች አሰማርቶ የነበረ መሆኑም ታውቋል።
በዘንድሮው የኢትዮጵያ 7ኛ አጠቃላይ ምርጫ ከ54 ሚሊዮን በላይ መራጮች የተመዘገቡ ሲሆን፣ ውድድሩ ከ547 የምርጫ ክልሎች ውስጥ በ501ዱ እና በአገር አቀፍ ደረጃ ባሉ 52 ሺህ ገደማ የምርጫ ጣቢያዎች ተካሂዷል።
ይሁን እንጂ በምርጫው ዕለት በጸጥታ ስጋት ምክንያት 143 የምርጫ ጣቢያዎች ሳይከፈቱ ቀርተዋል። በኦሮሚያ እና በአማራ ክልሎች፣ በተለይም እንደ ቢሎኖፓ፣ መቆሳቺ፣ ቀርሳ እና ኩታበር ባሉ አካባቢዎች ድምጽ አሰጣጥ ከተጀመረ በኋላ በጸጥታ እክሎች ምክንያት መቋረጡን ቦርዱ አስታውቋል። በትግራይ ክልል እንዲሁም በአማራና በኦሮሚያ አንዳንድ አካባቢዎች በጸጥታና በሎጅስቲክስ ምክንያት ድምጽ አልተሰጠም። ይህ ከመደረጉ በፊት ተቃዋሚዎችና ታዛቢዎች በእነዚህ አካባቢዎች ያለው ግጭት የመራጮችን ተሳትፎ ሊጎዳ እንደሚችል ስጋታቸውን ገልጸው ነበር። ምንም እንኳን እነዚህ መስተጓጎሎች ቢያጋጥሙም፣ በአብዛኛዎቹ የሀገሪቱ አካባቢዎች ድምጽ አሰጣጡ በሰላማዊ መንገድ የተጠናቀቀ ሲሆን፣ የዚህ ምርጫ የመጨረሻ ውጤት በመጪው ሰኔ 4 ቀን 2018 ዓ.ም ይፋ ይሆናል ተብሎ ይጠበቃል።
2 days ago
ኤርትራ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ጠቅላላ ጉባኤ ምክትል ፕሬዝዳንት ሆና ተመረጠች
#ethiopia | የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ጠቅላላ ጉባኤ በ85ኛው መደበኛ ስብሰባው ላይ በባለብዙ ወገን ዲፕሎማሲ ዙሪያ ያተኮሩ ቁልፍ አጀንዳዎችን የተወያየ ሲሆን፣ በስብሰባውም ለድርጅቱ 81ኛ ጠቅላላ ጉባኤ መሪ የሚሆኑትን አካላት መርጧል።
በዚህም መሰረት የምስራቅ አፍሪካዊቷ ሀገር ኤርትራ የከፍተኛ አባል ሀገራትን ድምጽ በማግኘት ከጠቅላላ ጉባኤው ምክትል ፕሬዝዳንቶች አንዷ ሆናለች::
ኤርትራ ከተመረጡ ሌሎች 16 አገራት ጋር በመሆን የጸጥታው ምክር ቤት አምስት ቋሚ አባላትን (ቻይና፣ ፈረንሳይ፣ ሩሲያ፣ ብሪታንያ እና አሜሪካ) በመቀላቀል የጠቅላላ ጉባኤውን ቢሮ በጋራ ትመራለች።
በተጨማሪም ከእሷ ጋር እንደ አፍጋኒስታን፣ ፊንላንድ፣ ግብፅ፣ ሊባኖስ፣ ፓራጓይ እና ዚምባብዌ ያሉ ሀገራትም በምክትል ፕሬዝዳንትነት መመረጣቸውን ለመረዳት ተችሏል።
በተመሳሳይ ዕለት በምስጢር በተካሄደው የድምፅ አሰጣጥ ሥነ-ሥርዓት፣ የወቅቱ የባንግላዲሽ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ካሊሉር ራህማን የ81ኛው ጠቅላላ ጉባኤ ፕሬዝዳንት ሆነው ተመርጠዋል
ሚስተር ራህማን 99 ድምጽ በማግኘት የተመረጡ ሲሆን፣ ተፎካካሪያቸውን የቆጵሮሱን አንድሪያስ ካኩሪስን በ91 ድምጽ አሸንፈዋል። በነሐሴ ወር መጨረሻ ላይ ሥራቸውን በይፋ የሚረከቡት ተመራጩ ፕሬዝዳንት ካሊሉር ራህማን ከአሸናፊነታቸው በኋላ ባደረጉት ንግግር፣ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በአሁኑ ወቅት ከባድ የፋይናንስ ቀውስ እና ዓለም አቀፍ የእምነት ማጣት ጉድለት እየገጠመው መሆኑን ጠቅሰው፣ አባል ሀገራቱ ድርጅቱ መለወጥና የተሻለ ውጤት ማምጣት እንደሚችል በተግባር ማሳየት እንዳለባቸውና በየብስ የሚደረገውን እያንዳንዱን አስተዋጽኦ ውጤታማ በማድረግ የጠፋውን እምነት መመለስ እንደሚገባ አሳስበዋል
ካፒታል ጋዜጣ
#ethiopia | የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ጠቅላላ ጉባኤ በ85ኛው መደበኛ ስብሰባው ላይ በባለብዙ ወገን ዲፕሎማሲ ዙሪያ ያተኮሩ ቁልፍ አጀንዳዎችን የተወያየ ሲሆን፣ በስብሰባውም ለድርጅቱ 81ኛ ጠቅላላ ጉባኤ መሪ የሚሆኑትን አካላት መርጧል።
በዚህም መሰረት የምስራቅ አፍሪካዊቷ ሀገር ኤርትራ የከፍተኛ አባል ሀገራትን ድምጽ በማግኘት ከጠቅላላ ጉባኤው ምክትል ፕሬዝዳንቶች አንዷ ሆናለች::
ኤርትራ ከተመረጡ ሌሎች 16 አገራት ጋር በመሆን የጸጥታው ምክር ቤት አምስት ቋሚ አባላትን (ቻይና፣ ፈረንሳይ፣ ሩሲያ፣ ብሪታንያ እና አሜሪካ) በመቀላቀል የጠቅላላ ጉባኤውን ቢሮ በጋራ ትመራለች።
በተጨማሪም ከእሷ ጋር እንደ አፍጋኒስታን፣ ፊንላንድ፣ ግብፅ፣ ሊባኖስ፣ ፓራጓይ እና ዚምባብዌ ያሉ ሀገራትም በምክትል ፕሬዝዳንትነት መመረጣቸውን ለመረዳት ተችሏል።
በተመሳሳይ ዕለት በምስጢር በተካሄደው የድምፅ አሰጣጥ ሥነ-ሥርዓት፣ የወቅቱ የባንግላዲሽ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ካሊሉር ራህማን የ81ኛው ጠቅላላ ጉባኤ ፕሬዝዳንት ሆነው ተመርጠዋል
ሚስተር ራህማን 99 ድምጽ በማግኘት የተመረጡ ሲሆን፣ ተፎካካሪያቸውን የቆጵሮሱን አንድሪያስ ካኩሪስን በ91 ድምጽ አሸንፈዋል። በነሐሴ ወር መጨረሻ ላይ ሥራቸውን በይፋ የሚረከቡት ተመራጩ ፕሬዝዳንት ካሊሉር ራህማን ከአሸናፊነታቸው በኋላ ባደረጉት ንግግር፣ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በአሁኑ ወቅት ከባድ የፋይናንስ ቀውስ እና ዓለም አቀፍ የእምነት ማጣት ጉድለት እየገጠመው መሆኑን ጠቅሰው፣ አባል ሀገራቱ ድርጅቱ መለወጥና የተሻለ ውጤት ማምጣት እንደሚችል በተግባር ማሳየት እንዳለባቸውና በየብስ የሚደረገውን እያንዳንዱን አስተዋጽኦ ውጤታማ በማድረግ የጠፋውን እምነት መመለስ እንደሚገባ አሳስበዋል
ካፒታል ጋዜጣ
Sponsored by
Surafel
2 days ago
♦️የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን የሚያዘጋጀው ዓመታዊው የግማሽ ማራትን ውድድር እሁድ ይካሄዳል
♦️የተሻለ ውጤት የሚያስመዘግቡ በዴንማርክ ኮፐንሃገን አለም አቀፍ ውድድር ላይ ይሳተፋሉ
እ.ኤ.አ አቆጣጠር ሴፔቴምበር 20 ይካሄዳል ተብሎ ለሚጠበቀው የአለም አትሌቲክስ ግማሽ ማራቶን ውድድር አትሌቶች በወንድም በሴቶችም የሚመረጡበት የአዲስ አበባ ግማሽ ማራቶን ውድድር የፊታችን እሁድ ይካሄዳል።
ጅማሬውንና ፍፃሜውን መስቀል አደባባይ የሚያደርገውና የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን በየዓመቱ የሚያከናውነው 19ኛው የ21 ኪ.ሜትር የጎዳና ላይ ውድድር በርካታ አትሌቶች በወንድም በሴትም የሚሳተፉበት ሲሆን በውድድሩ የተሻሉ ሆነው የሚያጠናቅቁ አትሌትች በሁለቱም ፃታ ሀገራቸውን ወክለው ሴፕቴምበር 20 በዴንማርክ ኮፐንሃገን የግማሽ ማራቶን ውድድር ላይ የሚያሳትፋቸውን ትኬት ይቆርጣሉ።
የአለም የግማሽ ማራቶን(የጎዳና ውድድርን)በሁለቱም ፆታ ሪከርዱን የያዙት ኢትዮጵያዊያን አቴሌቶች ሲሆኑ በወንዶች አትሌት ዮሚፍ ቀጄልቻ 57:30፣በሴቶች ደግሞ ለተሠንበት ግደይ 1:02:52 በሆነ ሠዓት በመግባትና በማሸነፍ የሪከርዱ ባለቤቶች ሆነዋል።
የአለም ግማሽ ማራቶን በዴንማርክ ኮፐንሃገን ሲካሄድ ከግማሽ ማራቶኑ በተጨማሪ የ5ኪ.ሜ እና የ1 ማይልስ ወይም የ1,609ኪ.ሜ ውድድርም እንደሚካሄድ ከተያዘው ፕሮግራም ለመረዳት ተችሏል።
ለሴፕቴምበር 20 የዴንማርክ ኮፐንሃገን የአለም አቀፍ ግማሽ ማራቶን የሚያሳልፈውን ትኬት የሚያስገኘው የአዲስ አበባው ግማሽ ማራቶን ውድድርን አስመልክቶ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን የፊታችን ዓርብ ጋዜጣዊ መግለጫ እንደሚሠጥ ቀይፋዊ የፌስቡክ ገፁ አሳውቋል።
✍️✍️በጋዜጠኛ ይስሀቅ በላይ(ሀትሪክ ስፖርት ኦፊሺያል)
♦️የተሻለ ውጤት የሚያስመዘግቡ በዴንማርክ ኮፐንሃገን አለም አቀፍ ውድድር ላይ ይሳተፋሉ
እ.ኤ.አ አቆጣጠር ሴፔቴምበር 20 ይካሄዳል ተብሎ ለሚጠበቀው የአለም አትሌቲክስ ግማሽ ማራቶን ውድድር አትሌቶች በወንድም በሴቶችም የሚመረጡበት የአዲስ አበባ ግማሽ ማራቶን ውድድር የፊታችን እሁድ ይካሄዳል።
ጅማሬውንና ፍፃሜውን መስቀል አደባባይ የሚያደርገውና የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን በየዓመቱ የሚያከናውነው 19ኛው የ21 ኪ.ሜትር የጎዳና ላይ ውድድር በርካታ አትሌቶች በወንድም በሴትም የሚሳተፉበት ሲሆን በውድድሩ የተሻሉ ሆነው የሚያጠናቅቁ አትሌትች በሁለቱም ፃታ ሀገራቸውን ወክለው ሴፕቴምበር 20 በዴንማርክ ኮፐንሃገን የግማሽ ማራቶን ውድድር ላይ የሚያሳትፋቸውን ትኬት ይቆርጣሉ።
የአለም የግማሽ ማራቶን(የጎዳና ውድድርን)በሁለቱም ፆታ ሪከርዱን የያዙት ኢትዮጵያዊያን አቴሌቶች ሲሆኑ በወንዶች አትሌት ዮሚፍ ቀጄልቻ 57:30፣በሴቶች ደግሞ ለተሠንበት ግደይ 1:02:52 በሆነ ሠዓት በመግባትና በማሸነፍ የሪከርዱ ባለቤቶች ሆነዋል።
የአለም ግማሽ ማራቶን በዴንማርክ ኮፐንሃገን ሲካሄድ ከግማሽ ማራቶኑ በተጨማሪ የ5ኪ.ሜ እና የ1 ማይልስ ወይም የ1,609ኪ.ሜ ውድድርም እንደሚካሄድ ከተያዘው ፕሮግራም ለመረዳት ተችሏል።
ለሴፕቴምበር 20 የዴንማርክ ኮፐንሃገን የአለም አቀፍ ግማሽ ማራቶን የሚያሳልፈውን ትኬት የሚያስገኘው የአዲስ አበባው ግማሽ ማራቶን ውድድርን አስመልክቶ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን የፊታችን ዓርብ ጋዜጣዊ መግለጫ እንደሚሠጥ ቀይፋዊ የፌስቡክ ገፁ አሳውቋል።
✍️✍️በጋዜጠኛ ይስሀቅ በላይ(ሀትሪክ ስፖርት ኦፊሺያል)
3 days ago
ምርጫው የኢትዮጵያ አሸናፊነት የተረጋገጠበት ነው፦ የአዲስ አበባ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት
#ethiopia | የአዲስ አበባ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የድምፅ አሰጣጥ ሂደትን መጠናቀቁን አስመልክቶ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቷል።
ምርጫው ከቅድመ ዝግጅት ጀምሮ ግልጽነት እና ፍትሐዊነት የተንጸባረቀበት፣ በመራጩ ሕዝብና በተፎካካሪ ፓርቲዎች ዘንድ ከፍተኛ ቅቡልነት ያገኘ መሆኑን በመግለጫው አስታውቋል።
ምክር ቤቱ በመግለጫው እንዳመለከተው ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም የተካሄደው ይህ ምርጫ መንግሥት በከተማዋ የዲሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ላይ ያለውን ቁርጠኝነት በተግባር ያሳየበትና የኢትዮጵያ አሸናፊነት የተረጋገጠበት ሌላኛው ታሪካዊ ምዕራፍ ሆኖ አልፏል።
ከእነዚህም መካከል እንደ ትልቅ ጅምር የሚወሰደው የዲጂታል የእጩዎች ምዝገባ ሒደት አላስፈላጊ መጉላላትን የቀነሰ እና የእጩዎችን መረጃ እና ደኅንነት ያረጋገጠ የአሰራ ግልፅነትን የፈጠረ መሆኑ በምርጫው ሂደት ከታዩ ዐበይት አዎንታዊ ሁነቶች መካከል እንደሆነ ተመላክቷል።
በምርጫው ዕለት መላው የከተማዋ ነዋሪዎች ከማለዳው 12 ሰዓት ጀምሮ ያለምንም ቀስቃሽ በነቂስ በመውጣት ድምፅ መስጠታቸውን የገለጸው ምክር ቤቱ፣ በተለይም ሴቶች፣ ወጣቶች እና አረጋውያን ያሳዩት ከፍተኛ ተነሳሽነት ሂደቱን ይበልጥ እንዳደመቀው አብራርቷል።
ከምርጫ ጣቢያዎች የሚመጡ የአሠራር ችግሮችን በጋራ በመገምገም፣ ከምርጫ ቦርድ እና ከከተማው አመራሮች ጋር በቀጥታ በመነጋገር አፋጣኝ የእርምት እርምጃ መወሰዱ በፓርቲዎች እና በአስፈፃሚ አካላት መካከል መተማመንን ማጎልበቱ ተገልጿል።
በተጨማሪም የከተማዋ የጸጥታ አካላት ያለምንም ወገንተኝነት፣ ፍጹም ገለልተኛ በሆነ መንገድ የምርጫ ጣቢያዎችን እና የመራጩን ሕዝብ ደኅንነት በመጠበቅ ላበረከቱት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ምክር ቤቱ ምስጋና አቅርቧል።
በሂደቱም ምንም ዓይነት የጸጥታ መደፍረስም ሆነ የምርጫ ሕግ መጣስ ሳይኖር መጠናቀቁ የከተማዋን ነዋሪዎችና የጸጥታ አካላት ከፍተኛ የበስለት ደረጃ ያሳየ "የአዲስ አበባ ሞዴል" መሆኑ ተነግሯል።
የድምፅ መስጠት ሂደቱ በስኬት ተጠናቅቆ ወደ ቀጣዩ የድምፅ ቆጠራ እና ውጤት ማደራጀት ምዕራፍ መሸጋገሩን የጠቀሰው ምክር ቤቱ፤ የምርጫ ቦርድ ሕጋዊ አሠራርን መሠረት አድርጎ የከተማውን ውጤት በኦፊሴላዊ መልኩ እስኪገልጽ ድረስ መላው የከተማዋ ነዋሪዎች፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች አባላት እና ደጋፊዎች ፍጹም በሆነ ትዕግሥት እንዲጠብቁ ጥሪ አቅርቧል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ethiopia #ethiopiaprevails #peace #ምርጫ
#ethiopia | የአዲስ አበባ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የድምፅ አሰጣጥ ሂደትን መጠናቀቁን አስመልክቶ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቷል።
ምርጫው ከቅድመ ዝግጅት ጀምሮ ግልጽነት እና ፍትሐዊነት የተንጸባረቀበት፣ በመራጩ ሕዝብና በተፎካካሪ ፓርቲዎች ዘንድ ከፍተኛ ቅቡልነት ያገኘ መሆኑን በመግለጫው አስታውቋል።
ምክር ቤቱ በመግለጫው እንዳመለከተው ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም የተካሄደው ይህ ምርጫ መንግሥት በከተማዋ የዲሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ላይ ያለውን ቁርጠኝነት በተግባር ያሳየበትና የኢትዮጵያ አሸናፊነት የተረጋገጠበት ሌላኛው ታሪካዊ ምዕራፍ ሆኖ አልፏል።
ከእነዚህም መካከል እንደ ትልቅ ጅምር የሚወሰደው የዲጂታል የእጩዎች ምዝገባ ሒደት አላስፈላጊ መጉላላትን የቀነሰ እና የእጩዎችን መረጃ እና ደኅንነት ያረጋገጠ የአሰራ ግልፅነትን የፈጠረ መሆኑ በምርጫው ሂደት ከታዩ ዐበይት አዎንታዊ ሁነቶች መካከል እንደሆነ ተመላክቷል።
በምርጫው ዕለት መላው የከተማዋ ነዋሪዎች ከማለዳው 12 ሰዓት ጀምሮ ያለምንም ቀስቃሽ በነቂስ በመውጣት ድምፅ መስጠታቸውን የገለጸው ምክር ቤቱ፣ በተለይም ሴቶች፣ ወጣቶች እና አረጋውያን ያሳዩት ከፍተኛ ተነሳሽነት ሂደቱን ይበልጥ እንዳደመቀው አብራርቷል።
ከምርጫ ጣቢያዎች የሚመጡ የአሠራር ችግሮችን በጋራ በመገምገም፣ ከምርጫ ቦርድ እና ከከተማው አመራሮች ጋር በቀጥታ በመነጋገር አፋጣኝ የእርምት እርምጃ መወሰዱ በፓርቲዎች እና በአስፈፃሚ አካላት መካከል መተማመንን ማጎልበቱ ተገልጿል።
በተጨማሪም የከተማዋ የጸጥታ አካላት ያለምንም ወገንተኝነት፣ ፍጹም ገለልተኛ በሆነ መንገድ የምርጫ ጣቢያዎችን እና የመራጩን ሕዝብ ደኅንነት በመጠበቅ ላበረከቱት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ምክር ቤቱ ምስጋና አቅርቧል።
በሂደቱም ምንም ዓይነት የጸጥታ መደፍረስም ሆነ የምርጫ ሕግ መጣስ ሳይኖር መጠናቀቁ የከተማዋን ነዋሪዎችና የጸጥታ አካላት ከፍተኛ የበስለት ደረጃ ያሳየ "የአዲስ አበባ ሞዴል" መሆኑ ተነግሯል።
የድምፅ መስጠት ሂደቱ በስኬት ተጠናቅቆ ወደ ቀጣዩ የድምፅ ቆጠራ እና ውጤት ማደራጀት ምዕራፍ መሸጋገሩን የጠቀሰው ምክር ቤቱ፤ የምርጫ ቦርድ ሕጋዊ አሠራርን መሠረት አድርጎ የከተማውን ውጤት በኦፊሴላዊ መልኩ እስኪገልጽ ድረስ መላው የከተማዋ ነዋሪዎች፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች አባላት እና ደጋፊዎች ፍጹም በሆነ ትዕግሥት እንዲጠብቁ ጥሪ አቅርቧል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ethiopia #ethiopiaprevails #peace #ምርጫ
4 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) "ለተፈጠረው ችግር ይቅርታ እንጠይቃለን" ሲሉ የምርጫ ቦርድ ሊቀመንበሯ ተናገሩ፡፡ የብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ሊቀመንበር ወይዘሮ ሜላት ወርቅ ሀይሉ የምርጫውን ሂደት አስመልክተው በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ በምድምፅ መስጫ ጣቢያዎች ለተፈጠረው ረጅም ሰልፍ ይቅርታ ጠይቀዋል፡፡ ችግሩ ሊፈጠር የቻለው በዲጂታል የተመዘገቡ መራጮች በርካታ በመሆናቸው የፊደል ቅደም ተከተል አሰራርና የካርድ ህትመት እጥረት በመፈጠሩ መሆኑን ጠቅሰው ካለዲጂታል የተመዘገቡ ግን ያለችግር እየተስተናገዱ እንደሚገኙ አስረድተዋል፡፡
ሊቀመንበሯ ዛሬ ከጠዋቱ 12 ሰአት ጀምሮ 50,800 ምርጫ ጣቢያዎች ተከፍተው ምርጫውን ማካሄዳቸውን ገልፀው 695ቱ ደግሞ ዘግይተው መከፈታቸውን አስታውቀዋል፡፡ እንዲሁም በ143 ምርጫ ጣቢያዎች ደግሞ በፀጥታ ችግር የተነሳ ምርጫ ማካሄድ ሳይቻል መቅረቱን ገልፀዋል፡፡
እነዚህ ምርጫ ያልተካሄደባቸው ጣቢያዎች በአማራና በኦሮሚያ ክልል የሚገኙ መሆናቸውን ያስታወቁት ሊቀመንበሯ ከእነዚህ መካከል ኩቻ፣ ሞኮሳና ቀርሳ እንደሚገኙበት ጠቅሰዋል፡፡ በዛሬው የምርጫ ሂደት አንድ የምርጫ ቦርድ አባል ህይወቱ ማለፉንም ወይዘሮ ሜላት ገልፀዋል፡፡ በነሞር ኢነር ምርጫ ክልል የምርጫ አስተባባሪ ሆነው የተመደቡት ግለሰብ በሞተር ሳይክል በደረሰባቸው አደጋ ህይወታቸው በማለፉ በምርጫ ቦርድ ስም የተሰማቸውን ሀዘን ገልፀዋል፡፡
ሊቀመንበሯ ዛሬ ከጠዋቱ 12 ሰአት ጀምሮ 50,800 ምርጫ ጣቢያዎች ተከፍተው ምርጫውን ማካሄዳቸውን ገልፀው 695ቱ ደግሞ ዘግይተው መከፈታቸውን አስታውቀዋል፡፡ እንዲሁም በ143 ምርጫ ጣቢያዎች ደግሞ በፀጥታ ችግር የተነሳ ምርጫ ማካሄድ ሳይቻል መቅረቱን ገልፀዋል፡፡
እነዚህ ምርጫ ያልተካሄደባቸው ጣቢያዎች በአማራና በኦሮሚያ ክልል የሚገኙ መሆናቸውን ያስታወቁት ሊቀመንበሯ ከእነዚህ መካከል ኩቻ፣ ሞኮሳና ቀርሳ እንደሚገኙበት ጠቅሰዋል፡፡ በዛሬው የምርጫ ሂደት አንድ የምርጫ ቦርድ አባል ህይወቱ ማለፉንም ወይዘሮ ሜላት ገልፀዋል፡፡ በነሞር ኢነር ምርጫ ክልል የምርጫ አስተባባሪ ሆነው የተመደቡት ግለሰብ በሞተር ሳይክል በደረሰባቸው አደጋ ህይወታቸው በማለፉ በምርጫ ቦርድ ስም የተሰማቸውን ሀዘን ገልፀዋል፡፡
4 days ago
በፀጥታ ችግር ምክንያት 143 የምርጫ ጣቢያዎች አለመከፈታቸውን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ገለጸ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በዛሬው ዕለት እየተካሄደ ያለውን ሰባተኛውን ጠቅላላ ምርጫ አስመልክቶ የቦርዱ ሰብሳቢ ወ/ሮ ሜላተወርቅ ኋይሉ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል።
በመግለጫቸውም በፀጥታ ችግር ምክንያት 143 የሚሆኑ የምርጫ ጣቢያዎች ምርጫ ሊደርግባቸው ዝግጅት ቢያደርጉም ያልተከፈቱ መሆናቸውን ገልጸዋል።
በአማራና በኦሮሚያ አንዳንድ አካባቢዎች ተከፍተው የተዘጉ እንደ ቀርሳ፣ ኩታበር፣ ቢሎኖፖ፣ መኮሳቺና ሌሎች አካባቢዎች የምርጫ ሂደቱ መቋረጡን ጠቁመዋል።
ከዚህ በተጨማሪ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው መራጮች ሰልፍ መሆናቸውን ያነሱት ዋና ሰብሳቢዋ በተለይም በድጅታል ምዝገባ የተመዘገቡ መራጮችን ላይ መዝግየቶች አሉ ብለዋል።
ችግሩን ለመፍታት እና መራጮች በፍጥነት ለማስተናገድ እየተሰራ መሆኑን ገልጸው ለተፈጠረው መጉላላት ይቅርታ ጠይቀዋል።
እንዲሁም በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ዘልመም እና ሰዳል አካባቢዎች የኔትወርክ ችግር በመኖሩ መረጃ ለመለዋወጥ ተግዳሮት መሆኑን ተናግረዋል።
#አሐዱ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በዛሬው ዕለት እየተካሄደ ያለውን ሰባተኛውን ጠቅላላ ምርጫ አስመልክቶ የቦርዱ ሰብሳቢ ወ/ሮ ሜላተወርቅ ኋይሉ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል።
በመግለጫቸውም በፀጥታ ችግር ምክንያት 143 የሚሆኑ የምርጫ ጣቢያዎች ምርጫ ሊደርግባቸው ዝግጅት ቢያደርጉም ያልተከፈቱ መሆናቸውን ገልጸዋል።
በአማራና በኦሮሚያ አንዳንድ አካባቢዎች ተከፍተው የተዘጉ እንደ ቀርሳ፣ ኩታበር፣ ቢሎኖፖ፣ መኮሳቺና ሌሎች አካባቢዎች የምርጫ ሂደቱ መቋረጡን ጠቁመዋል።
ከዚህ በተጨማሪ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው መራጮች ሰልፍ መሆናቸውን ያነሱት ዋና ሰብሳቢዋ በተለይም በድጅታል ምዝገባ የተመዘገቡ መራጮችን ላይ መዝግየቶች አሉ ብለዋል።
ችግሩን ለመፍታት እና መራጮች በፍጥነት ለማስተናገድ እየተሰራ መሆኑን ገልጸው ለተፈጠረው መጉላላት ይቅርታ ጠይቀዋል።
እንዲሁም በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ዘልመም እና ሰዳል አካባቢዎች የኔትወርክ ችግር በመኖሩ መረጃ ለመለዋወጥ ተግዳሮት መሆኑን ተናግረዋል።
#አሐዱ
5 days ago
ያከበረንን አክብረን የመረጠንን ሰርተንለት የምናልፍ ከሆነ ሁላችንም አሸናፊ እንሆናለን" ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
#ethiopia | ግንቦት 24፣ 2018 ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በትውልድ ቀያቸው በሻሻ ድምፅ ሰጥተዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በወቅቱ ለመገናኛ ብዙኃን እንደገለጹት፤ የኢትዮጵያ ህዝብ ከማለዳ ጀምሮ በመውጣት በሰልፍ ምርጫ እያካሄደ ይገኛል።
ይህም የሚሻውን ለመምረጥ መካሪ እንደማያስፈልገው ማሳያ መሆኑን ተናግረዋል። እኔ ዛሬ የሚያሳስበኝ ከመራጩ በላይ ተመራጩ ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ይህ ህዝብ በቁርጠኝነት የሚሻውን ወስኖ በዲሞክራሲያዊ መንገድ ከመረጠ በኋላ የተመረጡት ሰዎች በዚያ ልክ ታምነው እጃቸውና ልባቸው ንጹህ ሆኖ ደከመን ታከተን ሳይሉ ሰርተው የሀገር ታሪክ ለመቀየርና የህዝቡን ውለታ ለመክፈል ዝግጁነታቸው ምን ያክል ነው የሚለው ነው ሲሉ ተናግረዋል"
በምርጫው ሂደት ያሸነፉ በታማኝነት ማገልገል የተሸነፉ ደግሞ ውጤቱን በጸጋ ሊቀበሉ እንደሚገባ አሳስበዋል።
ጋዜጣ-ፕላስ
#የ7ኛውጠቅላላምርጫ #ምርጫ2018 #ሻሻ #ጠቅላይሚኒስትርዐቢይ #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | ግንቦት 24፣ 2018 ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በትውልድ ቀያቸው በሻሻ ድምፅ ሰጥተዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በወቅቱ ለመገናኛ ብዙኃን እንደገለጹት፤ የኢትዮጵያ ህዝብ ከማለዳ ጀምሮ በመውጣት በሰልፍ ምርጫ እያካሄደ ይገኛል።
ይህም የሚሻውን ለመምረጥ መካሪ እንደማያስፈልገው ማሳያ መሆኑን ተናግረዋል። እኔ ዛሬ የሚያሳስበኝ ከመራጩ በላይ ተመራጩ ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ይህ ህዝብ በቁርጠኝነት የሚሻውን ወስኖ በዲሞክራሲያዊ መንገድ ከመረጠ በኋላ የተመረጡት ሰዎች በዚያ ልክ ታምነው እጃቸውና ልባቸው ንጹህ ሆኖ ደከመን ታከተን ሳይሉ ሰርተው የሀገር ታሪክ ለመቀየርና የህዝቡን ውለታ ለመክፈል ዝግጁነታቸው ምን ያክል ነው የሚለው ነው ሲሉ ተናግረዋል"
በምርጫው ሂደት ያሸነፉ በታማኝነት ማገልገል የተሸነፉ ደግሞ ውጤቱን በጸጋ ሊቀበሉ እንደሚገባ አሳስበዋል።
ጋዜጣ-ፕላስ
#የ7ኛውጠቅላላምርጫ #ምርጫ2018 #ሻሻ #ጠቅላይሚኒስትርዐቢይ #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
10 days ago
በአማራ እና በትግራይ ክልሎች በ46 ምርጫ ክልሎች ምርጫ አይደረግም
ዛሬ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የቅድመ ምርጫ ሥራዎች እና የድምፅ መስጫ ቀንን አስመልክቶ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቷል።
በዚህም በአማራ እና በትግራይ ክልሎች በአጠቃላይ በ46 ምርጫ ክልሎች ምርጫ እንደማይደርግ አስታውቋል።
የቦርዱ ሰብሳቢ ወ/ሮ ሜላትወርቅ ሀይሉ፣ በአማራ ክልል በ8፣ በትግራይ ክልል ደግሞ በ38 የምርጫ ክልሎች ምርጫ እንደማይካሄድ ተናግረዋል።
በአማራ ክልል የት የት ነው የማይደረገው? ለሚለው ጥያቄ "ደቡብ ጎንደር፣ ምዕራብ ጎንደር፣ አምባሰል፣ ደጋዳሞት" እና የመሳሰሉት ምርጫ የማይደረግባቸው እንደሆነ ጠቁመዋል።
በተያያዘ ስድስት ፓርቲዎች ከዘንድሮው ምርጫ ከውድድር ውጭ በመሆናቸው የሚወዳደሩት ደግሞ 42 ፓርቲዎች ብቻ መሆናቸው ተገልጿል።
ከውድድሩ ውጭ የሆኑት ፓርቲዎች 3ቱ በትግራይ ክልል የሚንቀሳቀሱ፦
• ስምረት፣
• ቃንጪ ሀቂ
• ትንሳዔ ሰብዓ እንደርታ ፓርቲዎች መሆናቸውን ገልጸዋል።
ቀሪዎቹ ፦
• የኢትዮጵያ ሶሻል ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ኢሶዴፓ)፣
• የሲዳማ ፌደራሊስት ፓርቲ (ሲፌፓ)፣
• የጋምቤላ ሕዝቦች ነፃነት ንቅናቄ (ጋሕነን) መሆናቸውን ተናግረዋል።
Seledadotio
Seledadotio
ዛሬ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የቅድመ ምርጫ ሥራዎች እና የድምፅ መስጫ ቀንን አስመልክቶ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቷል።
በዚህም በአማራ እና በትግራይ ክልሎች በአጠቃላይ በ46 ምርጫ ክልሎች ምርጫ እንደማይደርግ አስታውቋል።
የቦርዱ ሰብሳቢ ወ/ሮ ሜላትወርቅ ሀይሉ፣ በአማራ ክልል በ8፣ በትግራይ ክልል ደግሞ በ38 የምርጫ ክልሎች ምርጫ እንደማይካሄድ ተናግረዋል።
በአማራ ክልል የት የት ነው የማይደረገው? ለሚለው ጥያቄ "ደቡብ ጎንደር፣ ምዕራብ ጎንደር፣ አምባሰል፣ ደጋዳሞት" እና የመሳሰሉት ምርጫ የማይደረግባቸው እንደሆነ ጠቁመዋል።
በተያያዘ ስድስት ፓርቲዎች ከዘንድሮው ምርጫ ከውድድር ውጭ በመሆናቸው የሚወዳደሩት ደግሞ 42 ፓርቲዎች ብቻ መሆናቸው ተገልጿል።
ከውድድሩ ውጭ የሆኑት ፓርቲዎች 3ቱ በትግራይ ክልል የሚንቀሳቀሱ፦
• ስምረት፣
• ቃንጪ ሀቂ
• ትንሳዔ ሰብዓ እንደርታ ፓርቲዎች መሆናቸውን ገልጸዋል።
ቀሪዎቹ ፦
• የኢትዮጵያ ሶሻል ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ኢሶዴፓ)፣
• የሲዳማ ፌደራሊስት ፓርቲ (ሲፌፓ)፣
• የጋምቤላ ሕዝቦች ነፃነት ንቅናቄ (ጋሕነን) መሆናቸውን ተናግረዋል።
Seledadotio
Seledadotio
10 days ago
በታገዱ ጣቢያዎች የተመዘገቡ መራጮች በልዩ ሁኔታ ድምፅ እንዲሰጡ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ወሰነ
ቀደም ሲል በተለያዩ ምክንያቶች በተዘጉ የምርጫ ጣቢያዎች ለተመዘገቡ መራጮች በምርጫው ዕለት ልዩ የምዝገባና የማረጋገጫ ሂደት ተካሂዶላቸው ድምፅ እንዲሰጡ መወሰኑን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አስታውቋል።
ቦርዱ ዛሬ ግንቦት 18 ቀን 2018 ዓ.ም. በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ፣ ውሳኔው የዜጎችን የመምረጥ ዴሞክራሲያዊ መብት ለማስከበርና ሂደቱን አካታች ለማድረግ ታስቦ የተወሰነ ነው ብሏል።
ቦርዱ ከዚህ ቀደም ባደረገው የክትትልና የማጣራት ሥራ የሕግ ጥሰት ተፈጽሞባቸዋል ያላቸውን 22 የምርጫ ጣቢያዎች አግዶ እንደነበር ይታወሳል።
እርምጃው የተወሰደባቸው እነዚህ ጣቢያዎች በ5 ክልሎች ማለትም፡- በኦሮሚያ 12፣ በሶማሌ 6፣ በሲዳማ 2፣ በአማራ 1፣ በሐረሪ ክልል 1 የምርጫ ጣቢያዎች ናቸው፡፡ የምርጫ ጣቢያዎቹ ሙሉ ለሙሉ ቢታገዱም፤ በእነዚህ የታገዱ ጣቢያዎች ውስጥ የተመዘገቡ ዜጎች መብታቸው ተጠብቆ በልዩ አሠራር ድምፅ የሚያስገቡበት ሁኔታ መመቻቸቱን ምርጫ ቦርድ ገልጾአል።
በፋሲል አረጋይ
ቀደም ሲል በተለያዩ ምክንያቶች በተዘጉ የምርጫ ጣቢያዎች ለተመዘገቡ መራጮች በምርጫው ዕለት ልዩ የምዝገባና የማረጋገጫ ሂደት ተካሂዶላቸው ድምፅ እንዲሰጡ መወሰኑን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አስታውቋል።
ቦርዱ ዛሬ ግንቦት 18 ቀን 2018 ዓ.ም. በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ፣ ውሳኔው የዜጎችን የመምረጥ ዴሞክራሲያዊ መብት ለማስከበርና ሂደቱን አካታች ለማድረግ ታስቦ የተወሰነ ነው ብሏል።
ቦርዱ ከዚህ ቀደም ባደረገው የክትትልና የማጣራት ሥራ የሕግ ጥሰት ተፈጽሞባቸዋል ያላቸውን 22 የምርጫ ጣቢያዎች አግዶ እንደነበር ይታወሳል።
እርምጃው የተወሰደባቸው እነዚህ ጣቢያዎች በ5 ክልሎች ማለትም፡- በኦሮሚያ 12፣ በሶማሌ 6፣ በሲዳማ 2፣ በአማራ 1፣ በሐረሪ ክልል 1 የምርጫ ጣቢያዎች ናቸው፡፡ የምርጫ ጣቢያዎቹ ሙሉ ለሙሉ ቢታገዱም፤ በእነዚህ የታገዱ ጣቢያዎች ውስጥ የተመዘገቡ ዜጎች መብታቸው ተጠብቆ በልዩ አሠራር ድምፅ የሚያስገቡበት ሁኔታ መመቻቸቱን ምርጫ ቦርድ ገልጾአል።
በፋሲል አረጋይ
Sponsored by
Surafel
11 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) በጣሊያን ሁለት የኢቦላ ተጠርጣሪዎች ተገኙ፡፡ በኡጋንዳ የእርዳታ ሰራተኛ የነበሩ ሁለት ጣሊያናዊያን ሚላን ከተማ ውስጥ በኢቦላ ተጠርጥረው ሆስፒታል መግባታቸው ተዘገበ፡፡ የ30 አመት እድሜ ያለው ወንድና የ31 አመቷ ሴት ከኡጋንዳ ወደአገራቸው የተመለሱት በአዲስ አበባ በኩል አድርገው መሆኑ ተገልጿል፡፡ ሚላን በደረሱበት ወቅት ከፍተኛ ትኩሳት፣ ማስመለስና ነስር ስለታየባቸው ሆስፒታል ገብተው በኳራንቲን ውስጥ እንደሚገኙ አንድ የጣሊያን ጋዜጣ ዘግቧል፡፡
ይህ በእንዲህ እንዳለ በዲሞክራቲክ ኮንጎ የኢቦላ ተጠርጣሪዎች ቁጥር 900 መድረሱን የአለም ጤና ድርጅት አስታውቋል፡፡ ከእነዚህ ውስጥ 101 ያህሉ በሽታው እንዳለባቸው የተረጋገጠ መሆኑንም አስረድቷል፡፡ በሌላ በኩል በኡጋንዳ ዛሬ በኢቦላ የተያዙ 2 ሰዎች የተገኙ ሲሆን ይህም በአገሪቱ ውስጥ በበሽታው የተያዙትን ቁጥር 7 አድርሶታል፡፡
ይህ በእንዲህ እንዳለ በዲሞክራቲክ ኮንጎ የኢቦላ ተጠርጣሪዎች ቁጥር 900 መድረሱን የአለም ጤና ድርጅት አስታውቋል፡፡ ከእነዚህ ውስጥ 101 ያህሉ በሽታው እንዳለባቸው የተረጋገጠ መሆኑንም አስረድቷል፡፡ በሌላ በኩል በኡጋንዳ ዛሬ በኢቦላ የተያዙ 2 ሰዎች የተገኙ ሲሆን ይህም በአገሪቱ ውስጥ በበሽታው የተያዙትን ቁጥር 7 አድርሶታል፡፡
12 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የምዕራባውያን አረንጓዴ ቴክኖሎጂ (Green-tech) እና የሎጂስቲክስ ኩባንያዎች በፍጥነት እያደገ ባለው የምስራቅ አፍሪካ የኢኮኖሚ ኮሪደር ውስጥ ቦታቸውን ለማረጋገጥ ሽሚያ ላይ ቢሆኑም፣ በአውሮፓ የፋይናንስ ተቋማት ዘንድ ያለው ስር የሰደደ የ'ስጋት ፍርሃት' ለትላልቅ የመሰረተ ልማት ኢንቨስትመንቶች ትልቅ ማነቆ መሆኑ ተጋልጧል። የኦስትሪያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ባለስልጣናት እንዳረጋገጡት፣ የግል የንግድ ባንኮች ከተለመደው የአውሮፓ ገበያ ውጪ በተለይም እንደ ኢትዮጵያ ባሉ በማደግ ላይ ባሉ ሀገራት ፋይናንስ ለማቅረብ ከፍተኛ ማቅማማት እያሳዩ ነው። ይህ ሁኔታ አውሮፓውያን በአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጠና የተፈጠረውን እምቅ የኢንቨስትመንት እድል በበቂ ሁኔታ እንዳይጠቀሙበት እንቅፋት ሆኖባቸዋል።
ችግሩ የፋይናንስ ተቋማቱ ፍርሃት ብቻ አይደለም፤ እጅግ የተንዛዛው የአውሮፓ ህብረት ቢሮክራሲም ሌላው የራስ ምታት ነው። ለአብነት ያህል፣ የአውሮፓ ህብረት የደን ጭፍጨፋን ለመከላከል ያወጣው አዲስ እና ጥብቅ ደንብ፣ በተለይም የኢትዮጵያን የግብርና ምርቶች ወደ አውሮፓ ለማስገባት እጅግ የተወሳሰበ የዲጂታል መከታተያ ስርዓትን ይጠይቃል። ይህንን መሰረተ ልማት ለመገንባት ህብረቱ 'ግሎባል ጌትዌይ' በተሰኘው መርሃ ግብሩ ከፍተኛ በጀት ቢመድብም፣ የኦስትሪያ የኢኮኖሚ የጀርባ አጥንት የሆኑት አነስተኛና መካከለኛ ኩባንያዎች የተወሳሰበውን የወረቀት ስራ እና የህብረቱን ቢሮክራሲ ማለፍ ባለመቻላቸው ከዕድሉ እየተገለሉ ይገኛሉ። የኦስትሪያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የንግድ አገልግሎት ክፍል ምክትል ዳይሬክተር ሮቤርቶ ቲም ይህንን እውነታ ለ'ካፒታል' ጋዜጣ አምነዋል።
ይህን መዋቅራዊ የፋይናንስ እና የቢሮክራሲ ማነቆ ለመስበር፣ የኦስትሪያ መንግስት "ቲም ኦስትሪያ" የሚል ጥምረት በመፍጠር ትናንሽ ኩባንያዎችን በአንድ ላይ የማሰባሰብ እና የግል ባንኮችን ፍርሃት ለመቀነስ መንግስታዊ የብድር ዋስትናዎችን የማመቻቸት ስራ መጀመሩን አስታውቋል። በሌላ በኩል ደግሞ፣ የአውሮፓ ህብረት ምክር ቤት በኢትዮጵያውያን ላይ ጥሎት የነበረውን ጥብቅ የሼንገን ቪዛ ክልከላ በማንሳት፣ የቪዛ አሰጣጡን ወደ መደበኛው የ15 ቀናት ሂደት እና መሰረታዊ የ80 ዩሮ ክፍያ መመለሱ የኦስትሪያ ባለስልጣናት የንግድ ግንኙነታቸውን ለማሳለጥ እንደ ጥሩ አጋጣሚ ወስደውታል። ሆኖም ይህ የቪዛ ማሻሻያ እና የፖሊሲ ለውጥ በተግባር የሚጠበቀውን የኢኮኖሚ ትብብር ሊያመጣ የሚችለው፣ የአውሮፓ ባንኮች ከተጣባባቸው የኢንቨስትመንት ስጋት እና ፍርሃት ሲላቀቁ ብቻ መሆኑን የዘርፉ ተንታኞች ይሞግታሉ።
ችግሩ የፋይናንስ ተቋማቱ ፍርሃት ብቻ አይደለም፤ እጅግ የተንዛዛው የአውሮፓ ህብረት ቢሮክራሲም ሌላው የራስ ምታት ነው። ለአብነት ያህል፣ የአውሮፓ ህብረት የደን ጭፍጨፋን ለመከላከል ያወጣው አዲስ እና ጥብቅ ደንብ፣ በተለይም የኢትዮጵያን የግብርና ምርቶች ወደ አውሮፓ ለማስገባት እጅግ የተወሳሰበ የዲጂታል መከታተያ ስርዓትን ይጠይቃል። ይህንን መሰረተ ልማት ለመገንባት ህብረቱ 'ግሎባል ጌትዌይ' በተሰኘው መርሃ ግብሩ ከፍተኛ በጀት ቢመድብም፣ የኦስትሪያ የኢኮኖሚ የጀርባ አጥንት የሆኑት አነስተኛና መካከለኛ ኩባንያዎች የተወሳሰበውን የወረቀት ስራ እና የህብረቱን ቢሮክራሲ ማለፍ ባለመቻላቸው ከዕድሉ እየተገለሉ ይገኛሉ። የኦስትሪያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የንግድ አገልግሎት ክፍል ምክትል ዳይሬክተር ሮቤርቶ ቲም ይህንን እውነታ ለ'ካፒታል' ጋዜጣ አምነዋል።
ይህን መዋቅራዊ የፋይናንስ እና የቢሮክራሲ ማነቆ ለመስበር፣ የኦስትሪያ መንግስት "ቲም ኦስትሪያ" የሚል ጥምረት በመፍጠር ትናንሽ ኩባንያዎችን በአንድ ላይ የማሰባሰብ እና የግል ባንኮችን ፍርሃት ለመቀነስ መንግስታዊ የብድር ዋስትናዎችን የማመቻቸት ስራ መጀመሩን አስታውቋል። በሌላ በኩል ደግሞ፣ የአውሮፓ ህብረት ምክር ቤት በኢትዮጵያውያን ላይ ጥሎት የነበረውን ጥብቅ የሼንገን ቪዛ ክልከላ በማንሳት፣ የቪዛ አሰጣጡን ወደ መደበኛው የ15 ቀናት ሂደት እና መሰረታዊ የ80 ዩሮ ክፍያ መመለሱ የኦስትሪያ ባለስልጣናት የንግድ ግንኙነታቸውን ለማሳለጥ እንደ ጥሩ አጋጣሚ ወስደውታል። ሆኖም ይህ የቪዛ ማሻሻያ እና የፖሊሲ ለውጥ በተግባር የሚጠበቀውን የኢኮኖሚ ትብብር ሊያመጣ የሚችለው፣ የአውሮፓ ባንኮች ከተጣባባቸው የኢንቨስትመንት ስጋት እና ፍርሃት ሲላቀቁ ብቻ መሆኑን የዘርፉ ተንታኞች ይሞግታሉ።
12 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የኢትዮጵያ መንግስት ለሀገር በቀል ባለሀብቶች ብቻ ተከልሎ የቆየውን ቁልፍ የሎጂስቲክስ ዘርፍ ሙሉ በሙሉ ለውጭ ባለሀብቶች ክፍት ለማድረግ የሚያስችል አዲስ መመሪያ አዘጋጅቷል። ይህ የቴሌኮም እና የፋይናንስ ዘርፎችን ፈለግ የተከተለው ውሳኔ፣ በሀገር ውስጥ የሎጂስቲክስ አቅራቢዎች ዘንድ ከፍተኛ ተቃውሞ እና ስጋት ፈጥሯል።
ትክክለኛ የትግበራ ቀኑ ባይገለጽም፣ አዲሱ መመሪያ ከቀጣዩ በጀት ዓመት መጀመሪያ አንስቶ ተግባራዊ ሊደረግ እንደሚችል ጉዳዩን በቅርበት የሚያውቁ ምንጮች ለ'ካፒታል' ጋዜጣ ገልጸዋል።
በኢትዮጵያ የሚንቀሳቀሱ የውጭ ባለሀብቶች የሎጂስቲክስ ዘርፉ ለስራቸው ትልቅ ማነቆ መሆኑን በተደጋጋሚ ሲያነሱ ቆይተዋል። ይህንንም ተከትሎ የተለያዩ ሀገራት እና የጥቅም ቡድኖች መንግስት ዘርፉን ክፍት እንዲያደርግ ከፍተኛ ግፊት ሲያደርጉ መቆየታቸው ይታወቃል።
ይሁን እንጂ የሀገር ውስጥ የሎጂስቲክስ ኦፕሬተሮች ይህን የመንግስት ውሳኔ አጥብቀው ይቃወማሉ። አቅራቢዎቹ ዘርፉ ለሀገሪቱ ኢኮኖሚ ማነቆ መሆኑን ቢያምኑም፣ መንግስት የዘርፉን እድገት በተመለከተ በቂ ግንዛቤ እና ትኩረት አለመስጠቱን ይወቅሳሉ። በተለይም የፋይናንስ እና የመድን አቅርቦት እጥረት፣ እንዲሁም ለኢንቨስትመንት የሚሆን መሬት አለማግኘት ለዘርፉ እድገት ትልቁን እንቅፋት እንደፈጠረ ይሞግታሉ።
የኢትዮጵያ የጭነት አስተላላፊዎች እና የመርከብ ወኪሎች ማህበር ፕሬዝዳንት እና የኮስሞስ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ዳዊት ውቤሸት፣ የገንዘብ ሚኒስትሩ አህመድ ሺዴ ዘርፉን ክፍት ለማድረግ መወሰኑን ማሳወቃቸውን አረጋግጠዋል። አቶ ዳዊት በወቅቱ ለሚኒስትሩ፣ "ዘርፉን ክፍት በማድረግ ሀገሪቱ የምታገኘው ተጨባጭ ጥቅም ምንድን ነው?" የሚል ጥያቄ ማቅረባቸውንም አስታውሰዋል።
በዘርፉ ላይ ጥልቅ እውቀት ያላቸው ባለሙያዎች፣ ኢትዮጵያ በዓመት ከ300,000 የማይበልጡ ኮንቴይነሮችን እንደምታስተናግድ ይገልጻሉ፤ ይህ መጠን ደግሞ በአንድ ትልቅ የቻይና የሎጂስቲክስ ኩባንያ በቀላሉ ሊሸፈን የሚችል ነው። በዚህም ምክንያት ትላልቅ ዓለም አቀፍ ኩባንያዎች ወደ ኢትዮጵያ ለመግባት ያን ያህል ፍላጎት ላይኖራቸው እንደሚችል ይገመታል።
የሀገር ውስጥ ኦፕሬተሮች፣ መንግስት እንደ ባንክ እና ቴሌኮም ዘርፍ ሁሉ የሎጂስቲክስ ዘርፉን አስቀድሞ ከለላ ሰጥቶ ማሳደግ ሲገባው፣ በቀጥታ ለውጭ ኩባንያዎች ክፍት ማድረጉ የሀገር ውስጥ ተቋማት በሞኖፖሊዎች እንዲዋጡ ያደርጋል የሚል ስጋት አላቸው።
አንዳንድ ታዛቢዎች ይህ የመንግስት ውሳኔ፣ ኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅትን ለመቀላቀል ካላት ፍላጎት ወይም የሎጂስቲክስ ኩባንያዎቻቸው ኢትዮጵያ ውስጥ መግባት ከሚፈልጉ የውጭ መንግስታት ጋር ከተገባ የፖለቲካ ቃል ኪዳን የመነጨ ሊሆን እንደሚችል ይገምታሉ።
ከሶስት ሳምንታት በፊት የወጣው የአሜሪካ የንግድ ተወካይ ጽህፈት ቤት ሪፖርት እንዳመለከተው፣ በኢትዮጵያ ያለው የሎጂስቲክስ ወጪ ከጠቅላላው የምርት ዋጋ ከ22 እስከ 27 በመቶውን ይይዛል። ይህ ብቻ ሳይሆን፣ የጭነት እና የማጓጓዣ ወጪው ከጎረቤት ሀገራት ጋር ሲነጻጸር በ60 በመቶ ብልጫ አለው።
መንግስት ቀደም ሲል የኢትዮጵያ ባህር ትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ብቻውን ይዞት የነበረውን የብዝሃ-ሞዳል ትራንስፖርት ሞኖፖሊ በማስቀረት ስድስት ተጨማሪ ኦፕሬተሮችን ፈቅዷል። ከዚህም ባሻገር የውጭ ኩባንያዎች እስከ 49 በመቶ ድርሻ እንዲኖራቸው መፍቀዱ ይታወሳል።
አሁን ደግሞ የደረቅ ወደቦችን፣ የጭነት ማስተላለፍ እና የሎጂስቲክስ አገልግሎቶችን ጨምሮ ቁልፍ የሎጂስቲክስ ንዑስ ዘርፎችን ሙሉ በሙሉ ክፍት ለማድረግ የሚያስችለውን የህግ ማዕቀፍ እስከ መጪው ታህሳስ ወር መጨረሻ እንደሚያጠናቅቅ መንግስት አረጋግጧል።
ትክክለኛ የትግበራ ቀኑ ባይገለጽም፣ አዲሱ መመሪያ ከቀጣዩ በጀት ዓመት መጀመሪያ አንስቶ ተግባራዊ ሊደረግ እንደሚችል ጉዳዩን በቅርበት የሚያውቁ ምንጮች ለ'ካፒታል' ጋዜጣ ገልጸዋል።
በኢትዮጵያ የሚንቀሳቀሱ የውጭ ባለሀብቶች የሎጂስቲክስ ዘርፉ ለስራቸው ትልቅ ማነቆ መሆኑን በተደጋጋሚ ሲያነሱ ቆይተዋል። ይህንንም ተከትሎ የተለያዩ ሀገራት እና የጥቅም ቡድኖች መንግስት ዘርፉን ክፍት እንዲያደርግ ከፍተኛ ግፊት ሲያደርጉ መቆየታቸው ይታወቃል።
ይሁን እንጂ የሀገር ውስጥ የሎጂስቲክስ ኦፕሬተሮች ይህን የመንግስት ውሳኔ አጥብቀው ይቃወማሉ። አቅራቢዎቹ ዘርፉ ለሀገሪቱ ኢኮኖሚ ማነቆ መሆኑን ቢያምኑም፣ መንግስት የዘርፉን እድገት በተመለከተ በቂ ግንዛቤ እና ትኩረት አለመስጠቱን ይወቅሳሉ። በተለይም የፋይናንስ እና የመድን አቅርቦት እጥረት፣ እንዲሁም ለኢንቨስትመንት የሚሆን መሬት አለማግኘት ለዘርፉ እድገት ትልቁን እንቅፋት እንደፈጠረ ይሞግታሉ።
የኢትዮጵያ የጭነት አስተላላፊዎች እና የመርከብ ወኪሎች ማህበር ፕሬዝዳንት እና የኮስሞስ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ዳዊት ውቤሸት፣ የገንዘብ ሚኒስትሩ አህመድ ሺዴ ዘርፉን ክፍት ለማድረግ መወሰኑን ማሳወቃቸውን አረጋግጠዋል። አቶ ዳዊት በወቅቱ ለሚኒስትሩ፣ "ዘርፉን ክፍት በማድረግ ሀገሪቱ የምታገኘው ተጨባጭ ጥቅም ምንድን ነው?" የሚል ጥያቄ ማቅረባቸውንም አስታውሰዋል።
በዘርፉ ላይ ጥልቅ እውቀት ያላቸው ባለሙያዎች፣ ኢትዮጵያ በዓመት ከ300,000 የማይበልጡ ኮንቴይነሮችን እንደምታስተናግድ ይገልጻሉ፤ ይህ መጠን ደግሞ በአንድ ትልቅ የቻይና የሎጂስቲክስ ኩባንያ በቀላሉ ሊሸፈን የሚችል ነው። በዚህም ምክንያት ትላልቅ ዓለም አቀፍ ኩባንያዎች ወደ ኢትዮጵያ ለመግባት ያን ያህል ፍላጎት ላይኖራቸው እንደሚችል ይገመታል።
የሀገር ውስጥ ኦፕሬተሮች፣ መንግስት እንደ ባንክ እና ቴሌኮም ዘርፍ ሁሉ የሎጂስቲክስ ዘርፉን አስቀድሞ ከለላ ሰጥቶ ማሳደግ ሲገባው፣ በቀጥታ ለውጭ ኩባንያዎች ክፍት ማድረጉ የሀገር ውስጥ ተቋማት በሞኖፖሊዎች እንዲዋጡ ያደርጋል የሚል ስጋት አላቸው።
አንዳንድ ታዛቢዎች ይህ የመንግስት ውሳኔ፣ ኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅትን ለመቀላቀል ካላት ፍላጎት ወይም የሎጂስቲክስ ኩባንያዎቻቸው ኢትዮጵያ ውስጥ መግባት ከሚፈልጉ የውጭ መንግስታት ጋር ከተገባ የፖለቲካ ቃል ኪዳን የመነጨ ሊሆን እንደሚችል ይገምታሉ።
ከሶስት ሳምንታት በፊት የወጣው የአሜሪካ የንግድ ተወካይ ጽህፈት ቤት ሪፖርት እንዳመለከተው፣ በኢትዮጵያ ያለው የሎጂስቲክስ ወጪ ከጠቅላላው የምርት ዋጋ ከ22 እስከ 27 በመቶውን ይይዛል። ይህ ብቻ ሳይሆን፣ የጭነት እና የማጓጓዣ ወጪው ከጎረቤት ሀገራት ጋር ሲነጻጸር በ60 በመቶ ብልጫ አለው።
መንግስት ቀደም ሲል የኢትዮጵያ ባህር ትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ብቻውን ይዞት የነበረውን የብዝሃ-ሞዳል ትራንስፖርት ሞኖፖሊ በማስቀረት ስድስት ተጨማሪ ኦፕሬተሮችን ፈቅዷል። ከዚህም ባሻገር የውጭ ኩባንያዎች እስከ 49 በመቶ ድርሻ እንዲኖራቸው መፍቀዱ ይታወሳል።
አሁን ደግሞ የደረቅ ወደቦችን፣ የጭነት ማስተላለፍ እና የሎጂስቲክስ አገልግሎቶችን ጨምሮ ቁልፍ የሎጂስቲክስ ንዑስ ዘርፎችን ሙሉ በሙሉ ክፍት ለማድረግ የሚያስችለውን የህግ ማዕቀፍ እስከ መጪው ታህሳስ ወር መጨረሻ እንደሚያጠናቅቅ መንግስት አረጋግጧል።
12 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) ናሚቢያ የኢትዮጵያ አየር መንገድን እርዳታ ጠየቀች፡፡ የናሚቢያ መንግስት ብሄራዊ አየር መንገዱን መልሶ ለማዋቀር የኢትዮጵያ አየር መንገድን እርዳታ መጠየቁ ተዘገበ፡፡ ይህንን ጥያቄ ተከትሎ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የቴክኒክ አዋጪነት ጥናት መጀመሩም ተገልጿል፡፡ ዋና ስራ አስፈፃሚው አቶ መስፍን ጣሰው ለፎርቹን ጋዜጣ ሲናገሩ ‹‹በመሰረተ ሀሳብ ደረጃ ድጋፍ ለማድረግ ተስማምተናል፡፡
ይሁንና የመጨረሻ ውሳኔያችንን በጥናት ውጤቱ ላይ የተመሰረተ ይሆናል›› ብለዋል፡፡ ጨምረውም እንዲህ አይነት ሌሎች የጥምረት ጥያቄዎች እየቀረቡላቸው መሆኑን ጠቅሰው ከሁለት ሌሎች ስማቸውን ካልጠቀሷቸው አገራት ጋር ንግግር እያደረጉ መሆኑን አስረድተዋል፡፡ የናሚቢያ አየር መንገድ እ.ኤ.አ በ2021 በኪሳራ ምክንያት ስራ ያቆመ መሆኑ ይታወቃል፡፡ ይህ ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ጋር የሚደረገው ንግግር የሚሳካ ከሆነ በሁለቱ አየር መንዶች ጥምረት ድጋሚ ወደበረራ የሚመለስ ይሆናል፡፡
ይሁንና የመጨረሻ ውሳኔያችንን በጥናት ውጤቱ ላይ የተመሰረተ ይሆናል›› ብለዋል፡፡ ጨምረውም እንዲህ አይነት ሌሎች የጥምረት ጥያቄዎች እየቀረቡላቸው መሆኑን ጠቅሰው ከሁለት ሌሎች ስማቸውን ካልጠቀሷቸው አገራት ጋር ንግግር እያደረጉ መሆኑን አስረድተዋል፡፡ የናሚቢያ አየር መንገድ እ.ኤ.አ በ2021 በኪሳራ ምክንያት ስራ ያቆመ መሆኑ ይታወቃል፡፡ ይህ ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ጋር የሚደረገው ንግግር የሚሳካ ከሆነ በሁለቱ አየር መንዶች ጥምረት ድጋሚ ወደበረራ የሚመለስ ይሆናል፡፡
12 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) በኢራን ከ100 በላይ ሙሽሮች በአንድ ላይ የተዳሩበት ‹‹ፒንክ›› የሰርግ ስነስርአት ተከናወነ፡፡ ባሳለፍነው ሳምንት በኢራን ዋና ከተማ ቴሄራን ለየት ያለ የሰርግ ስነስርአት መከናወኑን ዘታይምስ ጋዜጣ ዘግቧል፡፡ እንደዘገባው ይህንን የሰርግ ስነስርአት ያዘጋጀው የኢራን አብዮታዊ ዘብ ነው፡፡
ሙሽሮቹ በሙሉ ከእስራኤልና ከአሜሪካ ጋር በሚደረገው ጦርነት ተሰልፈው ለአገራቸው መስዋእትነትን ለመክፈል ፈቃደኛ የሆኑ መሆናቸውን የጠቀሰው ዘገባው የሰርግ ስነስርአቱ አስገራሚ ነገሮች እንደታዩበት አስታውቋል፡፡ ሁሉም ሙሽራና ሙሽሪት ፒንክ ቀለም ባላቸው ጂፕ መኪናዎች ውስጥ ተቀምጠው በከተማው ውስጥ ሲንሸራሸሩ የታዩ ሲሆን መኪናዎቹ ዲኮር የተደረጉትም በፒንክ አበባዎችና ፊኛዎች ነበር፡፡
በሁሉም የመኪናዎቹ የፊት መስታወት ላይ የቀድሞው የኢራን ጠቅላይ መሪ አያቶላ ሆሚኒና የልጃቸው የአሁኑ ጠቅላይ መሪ ፎቶዎች እንዲሰቀሉ መደረጋቸውን ያስታወቀው ዘገባው የአባትና ልጅ ምስል በፒንክ ቀለም የተሰራ መሆኑን አስረድቷል፡፡ ሙሽሮቹ በከተማው ውስጥ በሚዘዋወሩበት ወቅት በፒንክ ቀለም የተዘጋጁ የተለያዩ ጦር መሳሪያዎችን ይዘውም ታይተዋል፡፡ የሰርግ ስነስርአቱ 110 ጥንዶች በተገኙበት በቴሄራን በሚገኘው ፈርዶስ ፓርክ ውስጥ በደመቀ ስነስርአት በሚከናወንበት ወቅትም ፒንክ ቀለማት ብዙ ቦታዎች ላይ ጥቅም ላይ መዋላቸውን ዘገባው አስታውቋል፡፡
ሙሽሮቹ በሙሉ ከእስራኤልና ከአሜሪካ ጋር በሚደረገው ጦርነት ተሰልፈው ለአገራቸው መስዋእትነትን ለመክፈል ፈቃደኛ የሆኑ መሆናቸውን የጠቀሰው ዘገባው የሰርግ ስነስርአቱ አስገራሚ ነገሮች እንደታዩበት አስታውቋል፡፡ ሁሉም ሙሽራና ሙሽሪት ፒንክ ቀለም ባላቸው ጂፕ መኪናዎች ውስጥ ተቀምጠው በከተማው ውስጥ ሲንሸራሸሩ የታዩ ሲሆን መኪናዎቹ ዲኮር የተደረጉትም በፒንክ አበባዎችና ፊኛዎች ነበር፡፡
በሁሉም የመኪናዎቹ የፊት መስታወት ላይ የቀድሞው የኢራን ጠቅላይ መሪ አያቶላ ሆሚኒና የልጃቸው የአሁኑ ጠቅላይ መሪ ፎቶዎች እንዲሰቀሉ መደረጋቸውን ያስታወቀው ዘገባው የአባትና ልጅ ምስል በፒንክ ቀለም የተሰራ መሆኑን አስረድቷል፡፡ ሙሽሮቹ በከተማው ውስጥ በሚዘዋወሩበት ወቅት በፒንክ ቀለም የተዘጋጁ የተለያዩ ጦር መሳሪያዎችን ይዘውም ታይተዋል፡፡ የሰርግ ስነስርአቱ 110 ጥንዶች በተገኙበት በቴሄራን በሚገኘው ፈርዶስ ፓርክ ውስጥ በደመቀ ስነስርአት በሚከናወንበት ወቅትም ፒንክ ቀለማት ብዙ ቦታዎች ላይ ጥቅም ላይ መዋላቸውን ዘገባው አስታውቋል፡፡
12 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) ትናንት ቅዳሜ፣ ሜይ 23 ከዋይት ሀውስ ቅጥር ግቢ ውጪ በጸጥታ ኃይሎች በተወሰደ አጸፋዊ እርምጃ የተገደለው ታጣቂ ማንነት ይፋ መደረጉን የተለያዩ የዜና አውታሮች ዘገቡ። ሲኤንኤን እና ሲቢኤስ ኒውስ ለምርመራው ቅርበት ያላቸውን ምንጮች ጠቅሰው እንደዘገቡት፣ ተጠርጣሪው የ21 ዓመቱ ናስር ቤስት መሆኑ ተረጋግጧል። ግለሰቡ በ17ኛው ጎዳና እና ፔንሲልቬንያ አቬኑ አካባቢ ወደሚገኘው የዋይት ሀውስ ቅጥር ግቢ በመጠጋት ከቦርሳው ውስጥ የጦር መሳሪያ በማውጣት ተደጋጋሚ ተኩስ መክፈቱ ተገልጿል።
የሲክሬት ሰርቪስ ፖሊሶች በወሰዱት ፈጣን አጸፋዊ እርምጃ ተጠርጣሪው በጥይት ተመትቶ ወደ አካባቢው ሆስፒታል ቢወሰድም ህይወቱ ማለፉ ተረጋግጧል። በተኩስ ልውውጡ ወቅት አንድ በአቅራቢያው የነበረ አላፊ መንገደኛ በጥይት ተመትቶ ከባድ ጉዳት የደረሰበት ሲሆን፣ በጸጥታ ኃይሎች ላይ ግን ምንም አይነት ጉዳት አልተመዘገበም። በዋይት ሀውስ ውጪ ባለው የጥበቃ ኬላ ላይ ከ10 እስከ 20 የሚገመቱ ጥይቶች የተተኩሱ ሲሆን፣ ክስተቱን ተከትሎ ዋይት ሀውስ እስከ ምሽቱ 6:45 p.m. አካባቢ ድረስ የደህንነት እገዳ ተጥሎበት መቆየቱን ትናንት በዘ-ሐበሻ ዜና መዘገባችን አይዘነጋም።
የኤቢሲ ኒውስ የዋይት ሀውስ ዘጋቢ ሴሊና ዋንግ፣ የተኩሱ ድምጽ ሲሰማ መሬት ላይ ስትወድቅ የሚያሳይ ቪዲዮ በማህበራዊ ትስስር ገጿ ላይ አጋርታ፣ ደርዘን የሚሆኑ ጥይቶች ሲተኮሱ ይሰማ እንደነበር እና በፍጥነት ወደ ጋዜጣዊ መግለጫ መስጫ ክፍሉ እንዲሮጡ ታዘው እዚያው ተጠልለው መቆየታቸውን በማስፈራር የነበረውን አስፈሪ ድባብ ገልጻለች።
በጥቃቱ ወቅት ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በዋይት ሀውስ ውስጥ የነበሩ ቢሆንም ምንም አይነት አደጋ እንዳልደረሰባቸው የሲክሬት ሰርቪስ ቃል አቀባይ አረጋግጠዋል። ፕሬዝዳንቱ በ'ትሩዝ ሶሻል' ገጻቸው ባሰፈሩት መልእክት፣ ለአገሪቱ እጅግ የተከበረ ህንፃ ልዩ አባዜ በነበረውና የጥቃት ታሪክ ባለው ታጣቂ ላይ ለወሰዱት ፈጣን እና ሙያዊ እርምጃ ታላቁን የሲክሬት ሰርቪስ እና የህግ አስከባሪ አካላትን አመስግነዋል። ትራምፕ አክለውም፣ ይህ ክስተት ከዋይት ሀውስ የጋዜጠኞች እራት ግብዣ የተኩስ ጥቃት ከአንድ ወር በኋላ የተከሰተ መሆኑን አስታውሰው፣ የሀገሪቱ ብሄራዊ ደህንነት ለወደፊት ፕሬዝዳንቶች ይበልጥ ደህንነቱ የተጠበቀ ስፍራ መገንባትን አጥብቆ እንደሚጠይቅ አሳስበዋል።
በጸጥታ ኃይሎች የተገደለው ናስር ቤስት ከዚህ ቀደም ከዋይት ሀውስ ጋር የተያያዙ አሳሳቢ የህግ እና የስነ-ልቦና ሪከርዶች ነበሩት። በሰኔ 2025 በዋይት ሀውስ ምስራቃዊ ክፍል የተሽከርካሪ መግቢያን በመዝጋቱ ምክንያት አስገዳጅ በሆነ ሁኔታ ወደ አእምሮ ህክምና ማዕከል ገብቶ የነበረ ሲሆን፣ ወዲያውም በሀምሌ 2025 "እኔ ኢየሱስ ክርስቶስ ነኝ" በማለት ወደ ተከለከለው የዋይት ሀውስ ቅጥር ግቢ በመግባቱ በህገ-ወጥ ሰርጎ መግባት ወንጀል ታስሮ ነበር። በወቅቱም በተለያዩ የመግቢያ ኬላዎች ላይ እንዴት ሾልኮ መግባት እንደሚችል ሲጠያይቅ እንደነበር ሲክሬት ሰርቪስ አስተውሎ ነበር።
ከዚህ እስር በኋላ ወደ ዋይት ሀውስ አካባቢ እንዳይደርስ እገዳ የተጣለበት ቢሆንም፣ በነሐሴ ወር ፍርድ ቤት ሳይቀርብ በመቅረቱ የመያዣ ትዕዛዝ ወጥቶበት እንደነበር የፍርድ ቤት ሰነዶችን ጠቅሰው የዜና አውታሮቹ ዘግበዋል። ይህን የቅርብ ጊዜ ጥቃት በተመለከተ ከዋይት ሀውስ፣ ከሲክሬት ሰርቪስ እና ከኤፍቢአይ እስካሁን ተጨማሪ ማብራሪያ አልተሰጠም።
የሲክሬት ሰርቪስ ፖሊሶች በወሰዱት ፈጣን አጸፋዊ እርምጃ ተጠርጣሪው በጥይት ተመትቶ ወደ አካባቢው ሆስፒታል ቢወሰድም ህይወቱ ማለፉ ተረጋግጧል። በተኩስ ልውውጡ ወቅት አንድ በአቅራቢያው የነበረ አላፊ መንገደኛ በጥይት ተመትቶ ከባድ ጉዳት የደረሰበት ሲሆን፣ በጸጥታ ኃይሎች ላይ ግን ምንም አይነት ጉዳት አልተመዘገበም። በዋይት ሀውስ ውጪ ባለው የጥበቃ ኬላ ላይ ከ10 እስከ 20 የሚገመቱ ጥይቶች የተተኩሱ ሲሆን፣ ክስተቱን ተከትሎ ዋይት ሀውስ እስከ ምሽቱ 6:45 p.m. አካባቢ ድረስ የደህንነት እገዳ ተጥሎበት መቆየቱን ትናንት በዘ-ሐበሻ ዜና መዘገባችን አይዘነጋም።
የኤቢሲ ኒውስ የዋይት ሀውስ ዘጋቢ ሴሊና ዋንግ፣ የተኩሱ ድምጽ ሲሰማ መሬት ላይ ስትወድቅ የሚያሳይ ቪዲዮ በማህበራዊ ትስስር ገጿ ላይ አጋርታ፣ ደርዘን የሚሆኑ ጥይቶች ሲተኮሱ ይሰማ እንደነበር እና በፍጥነት ወደ ጋዜጣዊ መግለጫ መስጫ ክፍሉ እንዲሮጡ ታዘው እዚያው ተጠልለው መቆየታቸውን በማስፈራር የነበረውን አስፈሪ ድባብ ገልጻለች።
በጥቃቱ ወቅት ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በዋይት ሀውስ ውስጥ የነበሩ ቢሆንም ምንም አይነት አደጋ እንዳልደረሰባቸው የሲክሬት ሰርቪስ ቃል አቀባይ አረጋግጠዋል። ፕሬዝዳንቱ በ'ትሩዝ ሶሻል' ገጻቸው ባሰፈሩት መልእክት፣ ለአገሪቱ እጅግ የተከበረ ህንፃ ልዩ አባዜ በነበረውና የጥቃት ታሪክ ባለው ታጣቂ ላይ ለወሰዱት ፈጣን እና ሙያዊ እርምጃ ታላቁን የሲክሬት ሰርቪስ እና የህግ አስከባሪ አካላትን አመስግነዋል። ትራምፕ አክለውም፣ ይህ ክስተት ከዋይት ሀውስ የጋዜጠኞች እራት ግብዣ የተኩስ ጥቃት ከአንድ ወር በኋላ የተከሰተ መሆኑን አስታውሰው፣ የሀገሪቱ ብሄራዊ ደህንነት ለወደፊት ፕሬዝዳንቶች ይበልጥ ደህንነቱ የተጠበቀ ስፍራ መገንባትን አጥብቆ እንደሚጠይቅ አሳስበዋል።
በጸጥታ ኃይሎች የተገደለው ናስር ቤስት ከዚህ ቀደም ከዋይት ሀውስ ጋር የተያያዙ አሳሳቢ የህግ እና የስነ-ልቦና ሪከርዶች ነበሩት። በሰኔ 2025 በዋይት ሀውስ ምስራቃዊ ክፍል የተሽከርካሪ መግቢያን በመዝጋቱ ምክንያት አስገዳጅ በሆነ ሁኔታ ወደ አእምሮ ህክምና ማዕከል ገብቶ የነበረ ሲሆን፣ ወዲያውም በሀምሌ 2025 "እኔ ኢየሱስ ክርስቶስ ነኝ" በማለት ወደ ተከለከለው የዋይት ሀውስ ቅጥር ግቢ በመግባቱ በህገ-ወጥ ሰርጎ መግባት ወንጀል ታስሮ ነበር። በወቅቱም በተለያዩ የመግቢያ ኬላዎች ላይ እንዴት ሾልኮ መግባት እንደሚችል ሲጠያይቅ እንደነበር ሲክሬት ሰርቪስ አስተውሎ ነበር።
ከዚህ እስር በኋላ ወደ ዋይት ሀውስ አካባቢ እንዳይደርስ እገዳ የተጣለበት ቢሆንም፣ በነሐሴ ወር ፍርድ ቤት ሳይቀርብ በመቅረቱ የመያዣ ትዕዛዝ ወጥቶበት እንደነበር የፍርድ ቤት ሰነዶችን ጠቅሰው የዜና አውታሮቹ ዘግበዋል። ይህን የቅርብ ጊዜ ጥቃት በተመለከተ ከዋይት ሀውስ፣ ከሲክሬት ሰርቪስ እና ከኤፍቢአይ እስካሁን ተጨማሪ ማብራሪያ አልተሰጠም።
Sponsored by
Surafel
13 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) ከአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ መኖሪያ ዋይት ሀውስ ውጭ ባለው አካባቢ በጸጥታ አስከባሪዎች ላይ ተኩስ የከፈተ አንድ ግለሰብ መገደሉን የዩናይትድ ስቴትስ ሲክሬት ሰርቪስ አረጋገጠ።
ተቋሙ ባወጣው መግለጫ መሰረት፣ ቅዳሜ ከምሽቱ 12 ሰዓት (6:00 p.m) ጥቂት ደቂቃዎች ካለፉ በኋላ በ17ኛው ጎዳና እና ፔንሲልቬንያ አቬኑ አካባቢ አንድ ግለሰብ ከቦርሳው ውስጥ የጦር መሳሪያ በማውጣት መተኮስ ጀምሯል። በዚህ ጊዜ የሲክሬት ሰርቪስ ፖሊሶች አጸፋዊ ተኩስ በመክፈት ተጠርጣሪውን የመቱት ሲሆን፣ ግለሰቡ ወደ አካባቢው ሆስፒታል ቢወሰድም ህይወቱ ማለፉ ተረጋግጧል። በዚሁ የተኩስ ልውውጥ ወቅት በአካባቢው የነበረ አንድ አላፊ መንገደኛም በጥይት መመታቱ ታውቋል።
በጥቃቱ በጸጥታ አስከባሪዎች ላይ ምንም አይነት ጉዳት አልደረሰም። ክስተቱ ሲፈጠር ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በዋይት ሀውስ ውስጥ የነበሩ ቢሆንም፣ በእርሳቸውም ሆነ በሌሎች ጥበቃ በሚደረግላቸው ግለሰቦች እና አጠቃላይ የስራ እንቅስቃሴ ላይ የፈጠረው ተጽዕኖ የለም። በወቅቱ በስፍራው የነበሩ ጋዜጠኞች ተከታታይ የተኩስ ድምጽ መስማታቸውን ተከትሎ፣ የሲክሬት ሰርቪስ አባላት በፍጥነት ወደ ጋዜጣዊ መግለጫ መስጫ ክፍል ያስገቧቸው ሲሆን ዋይት ሀውስም ለተወሰነ ጊዜ የደህንነት እገዳ ተጥሎበት ቆይቷል። ይህ እገዳ ከምሽቱ 1 ሰዓት ላይ ተነስቷል።
ለሲቢኤስ ኒውስ የደረሱ መረጃዎች እንደሚያመለክቱት፣ በአጠቃላይ ከ15 እስከ 30 የሚደርሱ ጥይቶች ተተኩሰዋል። የታጠቀው ግለሰብ ወደ ሲክሬት ሰርቪስ ወኪሎች በመጠጋት ተኩስ ቢከፍትም ሳይሳካለት ቀርቶ የአጸፋ እርምጃ ተወስዶበታል።
ይህ አስደንጋጭ ክስተት የተፈጠረው፣ የዋይት ሀውስ የጋዜጠኞች ማህበር እራት ግብዣ ላይ ተመሳሳይ የተኩስ ጥቃት ከተፈጸመ ከአንድ ወር በኋላ መሆኑ ሁኔታውን ይበልጥ አሳሳቢ አድርጎታል። ክስተቱ በነበረበት ወቅት በዋይት ሀውስ ውስጥ ከነበሩት ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በኩል እስካሁን የተሰጠ አስተያየት የለም።
ተቋሙ ባወጣው መግለጫ መሰረት፣ ቅዳሜ ከምሽቱ 12 ሰዓት (6:00 p.m) ጥቂት ደቂቃዎች ካለፉ በኋላ በ17ኛው ጎዳና እና ፔንሲልቬንያ አቬኑ አካባቢ አንድ ግለሰብ ከቦርሳው ውስጥ የጦር መሳሪያ በማውጣት መተኮስ ጀምሯል። በዚህ ጊዜ የሲክሬት ሰርቪስ ፖሊሶች አጸፋዊ ተኩስ በመክፈት ተጠርጣሪውን የመቱት ሲሆን፣ ግለሰቡ ወደ አካባቢው ሆስፒታል ቢወሰድም ህይወቱ ማለፉ ተረጋግጧል። በዚሁ የተኩስ ልውውጥ ወቅት በአካባቢው የነበረ አንድ አላፊ መንገደኛም በጥይት መመታቱ ታውቋል።
በጥቃቱ በጸጥታ አስከባሪዎች ላይ ምንም አይነት ጉዳት አልደረሰም። ክስተቱ ሲፈጠር ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በዋይት ሀውስ ውስጥ የነበሩ ቢሆንም፣ በእርሳቸውም ሆነ በሌሎች ጥበቃ በሚደረግላቸው ግለሰቦች እና አጠቃላይ የስራ እንቅስቃሴ ላይ የፈጠረው ተጽዕኖ የለም። በወቅቱ በስፍራው የነበሩ ጋዜጠኞች ተከታታይ የተኩስ ድምጽ መስማታቸውን ተከትሎ፣ የሲክሬት ሰርቪስ አባላት በፍጥነት ወደ ጋዜጣዊ መግለጫ መስጫ ክፍል ያስገቧቸው ሲሆን ዋይት ሀውስም ለተወሰነ ጊዜ የደህንነት እገዳ ተጥሎበት ቆይቷል። ይህ እገዳ ከምሽቱ 1 ሰዓት ላይ ተነስቷል።
ለሲቢኤስ ኒውስ የደረሱ መረጃዎች እንደሚያመለክቱት፣ በአጠቃላይ ከ15 እስከ 30 የሚደርሱ ጥይቶች ተተኩሰዋል። የታጠቀው ግለሰብ ወደ ሲክሬት ሰርቪስ ወኪሎች በመጠጋት ተኩስ ቢከፍትም ሳይሳካለት ቀርቶ የአጸፋ እርምጃ ተወስዶበታል።
ይህ አስደንጋጭ ክስተት የተፈጠረው፣ የዋይት ሀውስ የጋዜጠኞች ማህበር እራት ግብዣ ላይ ተመሳሳይ የተኩስ ጥቃት ከተፈጸመ ከአንድ ወር በኋላ መሆኑ ሁኔታውን ይበልጥ አሳሳቢ አድርጎታል። ክስተቱ በነበረበት ወቅት በዋይት ሀውስ ውስጥ ከነበሩት ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በኩል እስካሁን የተሰጠ አስተያየት የለም።
14 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) ‹‹በዚህ አመት ብቻ ሩሲያ 145,000 ወታደሮቿን አጥታለች›› ሲሉ ዘለንስኪ ተናገሩ፡፡ የዩክሬይኑ ፕሬዝደንት ዘለንስኪ በያዝነው የፈረንጆች አመት ማለትም በ20206 ብቻ ሩሲያ 145,000 ወታደሮቿን ማጣቷን ሲገልፁ ከእነዚህ መካከል ወደ86,000 ያህሉ የተገደሉ መሆናቸውን አስታውቀዋል፡፡ ፕሬዝደንቱ በዛሬው እለት ከጦር ሀይል ዋና አዛዥ ኦሌክሳንደር ሲሪስኪ ጋር ከተወያዩ በኋላ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ይህንን ቁጥር የጠሩ ሲሆን በተጨማሪም ቢያንስ 59,000 ወታደሮች በፅኑ መቁሰላቸውንና 800 ደግሞ ምርኮኛ መሆናቸውንም ገልፀዋል፡፡
የዩክሬይን ወታደሮች በሩሲያ ላይ የሚያደርጉትን ዘመቻ ቀጥለው በወታደሮች ላይ ብቻም ሳይሆን በቁሳቁሶች ላይ ከፍተኛ ጉዳት ማድረሳቸውን ያስታወቁት ዘለንስኪ በተለይ ከሩሲያ ጋር በሚዋሰነው ሱሚ ግዛት ከፍተኛ ድል መቀዳጀታቸውን ገልፀዋል፡፡ ሲናገሩም ‹‹በድንበር አቅራቢያ በሚገኘው ሱሚ ግዛት የፈለግነውን ግብ አሳክተናል›› ብለዋል፡፡ ፕሬዝደንቱ ይህ ጦርነት ከተጀመረ አንስቶ በሩሲያ ወታደሮች ላይ የደረሰው ጉዳት 1,353,860 መሆኑን ጠቅሰው በትላንትናው እለት ብቻ 800 ወታደሮች መገደላቸውን አስታውቀዋል፡፡
ይህ በእንዲህ እንዳለ የቢቢሲ ሩሲያ አገልግሎት አደረኩት ባለው ማጣራት ጦርነቱ ከተጀመረ አንስቶ የሞቱት የሩሲያ ወታደሮች ቁጥር 217,808 መሆኑን ገልጿል፡፡ በተያያዘ ዜና ዘለንስኪ በዛሬው እለት በሩሲያ ውስጥ 700 ኪሎ ሜትር ዘልቀው በመግባት በአንድ ነዳጅ ማጣሪያ ላይ ጥቃት መፈፀማቸውን ገልፀዋል፡፡ በኤክስ ገፃቸው ላይም ‹‹አሁን ጦርነቱን ወደሩሲያ ውስጥ እየከተትነው ነው፡፡ ይህ ደግሞ ተገቢ ነው›› ብለዋል፡፡
የዩክሬይን ወታደሮች በሩሲያ ላይ የሚያደርጉትን ዘመቻ ቀጥለው በወታደሮች ላይ ብቻም ሳይሆን በቁሳቁሶች ላይ ከፍተኛ ጉዳት ማድረሳቸውን ያስታወቁት ዘለንስኪ በተለይ ከሩሲያ ጋር በሚዋሰነው ሱሚ ግዛት ከፍተኛ ድል መቀዳጀታቸውን ገልፀዋል፡፡ ሲናገሩም ‹‹በድንበር አቅራቢያ በሚገኘው ሱሚ ግዛት የፈለግነውን ግብ አሳክተናል›› ብለዋል፡፡ ፕሬዝደንቱ ይህ ጦርነት ከተጀመረ አንስቶ በሩሲያ ወታደሮች ላይ የደረሰው ጉዳት 1,353,860 መሆኑን ጠቅሰው በትላንትናው እለት ብቻ 800 ወታደሮች መገደላቸውን አስታውቀዋል፡፡
ይህ በእንዲህ እንዳለ የቢቢሲ ሩሲያ አገልግሎት አደረኩት ባለው ማጣራት ጦርነቱ ከተጀመረ አንስቶ የሞቱት የሩሲያ ወታደሮች ቁጥር 217,808 መሆኑን ገልጿል፡፡ በተያያዘ ዜና ዘለንስኪ በዛሬው እለት በሩሲያ ውስጥ 700 ኪሎ ሜትር ዘልቀው በመግባት በአንድ ነዳጅ ማጣሪያ ላይ ጥቃት መፈፀማቸውን ገልፀዋል፡፡ በኤክስ ገፃቸው ላይም ‹‹አሁን ጦርነቱን ወደሩሲያ ውስጥ እየከተትነው ነው፡፡ ይህ ደግሞ ተገቢ ነው›› ብለዋል፡፡
14 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) በዱባይ ከህግ እይታ ውጭ በድብቅ የሚካሄደው የሴተኛ አዳሪነት (ኤስኮርት) ኢንዱስትሪ፣ በቀጠናው ያለው የጦርነት ውጥረት ሳይበግረው አሁንም በስፋት እየተካሄደ መሆኑን አንድ አዲስ የምርመራ ዘገባ አጋለጠ። 'ዘ ሰን' ጋዜጣ ያወጣው ይህ የምርመራ ዘገባ እንዳመለከተው፣ ዝሙት አዳሪነት በህግ የተከለከለባት እስላማዊ ሀገር ብትሆንም የኤሚሬትስቱ ከተማ ዱባይ የበርካታ ዓለም አቀፍ የሴተኛ አዳሪዎች ዋነኛ ማዕከል ሆና ቀጥላለች።
ምርመራው እንዳረጋገጠው፣ በቅርቡ አሜሪካ እና እስራኤል በመካከለኛው ምስራቅ ካደረጉት ወታደራዊ እንቅስቃሴ ጋር ተያይዞ ኢራን በኤሚሬትስ ላይ ወታደራዊ እርምጃዎችን ብትወስድም፣ በዱባይ ለሴተኛ አዳሪዎች የሚወጡ ማስታወቂያዎች ቁጥር አስገራሚ በሆነ ሁኔታ 10,366 ደርሷል። ይህ አሃዝ ኤሚሬትስን በዓለም አቀፍ ደረጃ በሴተኛ አዳሪዎች ማስታወቂያ 2ኛ ደረጃ ላይ እንድትቀመጥ አድርጓታል። በሚስጥራዊ የመስመር ላይ መድረኮች ላይ ደንበኞች በአሁኑ የጦርነት ውጥረት ውስጥ አገልግሎቱ መኖር አለመኖሩን ብለው ለሚጠይቁት ጥያቄ፣ ንግዱ አሁንም እንደ ቀድሞው እየተካሄደ ነው የሚል ምላሽ እንደተሰጣቸው ዘገባው አጋልጧል።
እንደ ኢትዮጵያ፣ ኢራን፣ እና ቤላሩስ ካሉ የተለያዩ ሀገራት የተውጣጡ ሴተኛ አዳሪዎች በከተማዋ በስፋት የሚገኙ ሲሆን፣ አብዛኛዎቹ በሰዓት በመቶዎች የሚቆጠሩ ዶላሮችን ያስከፍላሉ። ለዋጋ ማሳያነት በምርመራው 'ጃና' በሚል ስም የተጠቀሰች አንዲት የ27 ዓመት ቤላሩሳዊት ሴት፣ ለ48 ሰዓታት አገልግሎት እስከ 4,000 ዶላር እንደምትጠይቅ እና ለተጨማሪ ልዩ አገልግሎቶች ደግሞ የ375 ዶላር ተጨማሪ ክፍያ እንደምታስከፍል ታውቋል።
በተጨማሪም ሌሎች ድረ-ገጾች እንደ ማሳጅ እና ከደንበኞች ጋር የፍቅር ግንኙነት እንዳላቸው አድርገው የሚተወኑበትን 'የፍቅረኛነት ልምድ' የተሰኘ አገልግሎት የሚያቀርቡ በሺዎች የሚቆጠሩ ማስታወቂያዎችን ይዘው ተገኝተዋል። ለነዚህ አገልግሎቶች በሰዓት ከ400 ዶላር በላይ ያስከፍላሉ። በመስመር ላይ መድረኮች ላይም አንዲት ክፍያዋ ከ355 እስከ 500 ዶላር የሚደርስ ቦሊቪያዊት ሴተኛ አዳሪ፣ ደንበኞቿ በጣም ተግባቢ እና የማትቸኩል መሆኗን በመግለጽ አድናቆታቸውን ሲሰጧት ታይታለች። እሷም በቅርቡ ለተጨማሪ የፍቅር ጨዋታ እንገናኝ ስትል በአደባባይ ምላሽ ሰጥታለች።
ምንም እንኳን ይህ ድብቅ ገበያ ማደጉን ቢቀጥልም፣ በተባበሩት አረብ ኤሚሬትስ ዝሙት አዳሪነት አሁንም ሙሉ በሙሉ በህግ የተከለከለ ነው። ሀገሪቱ በ2020 እ.ኤ.አ. ላላገቡ ጥንዶች አብሮ የመኖር መብትን ብትፈቅድም፤ ሴተኛ አዳሪነት፣ አገናኝነት እና የዝሙት ቤቶችን ማስተዳደር ከባድ ወንጀሎች ናቸው። ድርጊቱ እስራት፣ የገንዘብ ቅጣት እና ከሀገር መባረርን ያስከትላል። የሰው ማዘዋወር ወንጀሎች ደግሞ በከባድ ሁኔታዎች እስከ ዕድሜ ልክ እስራት ሊያስቀጡ ይችላሉ።
የዱባይ ፖሊስ በህገ-ወጥ የሴተኛ አዳሪነት መረቦች፣ የማሳጅ ቤቶች እና የ'ኤስኮርት' አገልግሎቶች ላይ ተደጋጋሚ ኦፕሬሽኖችን በማካሄድ የውጭ ዜጋ የሆኑ ሴቶችን በቁጥጥር ስር በማዋል ከሀገር እያባረረ ይገኛል። በተጨማሪም፣ በመንገድ ላይ እና በመኪናዎች ላይ የሚበተኑ የሴተኛ አዳሪ ማስታወቂያ ካርዶችን ለማስቆም፣ እንዲሁም የተደራጀ የሴተኛ አዳሪነት ንግድን እና የብልግና ድርጊቶችን ለመዋጋት የጸረ-ሰው ማዘዋወር ልዩ ክፍሎችን በማቋቋም እርምጃውን አጠናክሮ ቀጥሏል።
ምርመራው እንዳረጋገጠው፣ በቅርቡ አሜሪካ እና እስራኤል በመካከለኛው ምስራቅ ካደረጉት ወታደራዊ እንቅስቃሴ ጋር ተያይዞ ኢራን በኤሚሬትስ ላይ ወታደራዊ እርምጃዎችን ብትወስድም፣ በዱባይ ለሴተኛ አዳሪዎች የሚወጡ ማስታወቂያዎች ቁጥር አስገራሚ በሆነ ሁኔታ 10,366 ደርሷል። ይህ አሃዝ ኤሚሬትስን በዓለም አቀፍ ደረጃ በሴተኛ አዳሪዎች ማስታወቂያ 2ኛ ደረጃ ላይ እንድትቀመጥ አድርጓታል። በሚስጥራዊ የመስመር ላይ መድረኮች ላይ ደንበኞች በአሁኑ የጦርነት ውጥረት ውስጥ አገልግሎቱ መኖር አለመኖሩን ብለው ለሚጠይቁት ጥያቄ፣ ንግዱ አሁንም እንደ ቀድሞው እየተካሄደ ነው የሚል ምላሽ እንደተሰጣቸው ዘገባው አጋልጧል።
እንደ ኢትዮጵያ፣ ኢራን፣ እና ቤላሩስ ካሉ የተለያዩ ሀገራት የተውጣጡ ሴተኛ አዳሪዎች በከተማዋ በስፋት የሚገኙ ሲሆን፣ አብዛኛዎቹ በሰዓት በመቶዎች የሚቆጠሩ ዶላሮችን ያስከፍላሉ። ለዋጋ ማሳያነት በምርመራው 'ጃና' በሚል ስም የተጠቀሰች አንዲት የ27 ዓመት ቤላሩሳዊት ሴት፣ ለ48 ሰዓታት አገልግሎት እስከ 4,000 ዶላር እንደምትጠይቅ እና ለተጨማሪ ልዩ አገልግሎቶች ደግሞ የ375 ዶላር ተጨማሪ ክፍያ እንደምታስከፍል ታውቋል።
በተጨማሪም ሌሎች ድረ-ገጾች እንደ ማሳጅ እና ከደንበኞች ጋር የፍቅር ግንኙነት እንዳላቸው አድርገው የሚተወኑበትን 'የፍቅረኛነት ልምድ' የተሰኘ አገልግሎት የሚያቀርቡ በሺዎች የሚቆጠሩ ማስታወቂያዎችን ይዘው ተገኝተዋል። ለነዚህ አገልግሎቶች በሰዓት ከ400 ዶላር በላይ ያስከፍላሉ። በመስመር ላይ መድረኮች ላይም አንዲት ክፍያዋ ከ355 እስከ 500 ዶላር የሚደርስ ቦሊቪያዊት ሴተኛ አዳሪ፣ ደንበኞቿ በጣም ተግባቢ እና የማትቸኩል መሆኗን በመግለጽ አድናቆታቸውን ሲሰጧት ታይታለች። እሷም በቅርቡ ለተጨማሪ የፍቅር ጨዋታ እንገናኝ ስትል በአደባባይ ምላሽ ሰጥታለች።
ምንም እንኳን ይህ ድብቅ ገበያ ማደጉን ቢቀጥልም፣ በተባበሩት አረብ ኤሚሬትስ ዝሙት አዳሪነት አሁንም ሙሉ በሙሉ በህግ የተከለከለ ነው። ሀገሪቱ በ2020 እ.ኤ.አ. ላላገቡ ጥንዶች አብሮ የመኖር መብትን ብትፈቅድም፤ ሴተኛ አዳሪነት፣ አገናኝነት እና የዝሙት ቤቶችን ማስተዳደር ከባድ ወንጀሎች ናቸው። ድርጊቱ እስራት፣ የገንዘብ ቅጣት እና ከሀገር መባረርን ያስከትላል። የሰው ማዘዋወር ወንጀሎች ደግሞ በከባድ ሁኔታዎች እስከ ዕድሜ ልክ እስራት ሊያስቀጡ ይችላሉ።
የዱባይ ፖሊስ በህገ-ወጥ የሴተኛ አዳሪነት መረቦች፣ የማሳጅ ቤቶች እና የ'ኤስኮርት' አገልግሎቶች ላይ ተደጋጋሚ ኦፕሬሽኖችን በማካሄድ የውጭ ዜጋ የሆኑ ሴቶችን በቁጥጥር ስር በማዋል ከሀገር እያባረረ ይገኛል። በተጨማሪም፣ በመንገድ ላይ እና በመኪናዎች ላይ የሚበተኑ የሴተኛ አዳሪ ማስታወቂያ ካርዶችን ለማስቆም፣ እንዲሁም የተደራጀ የሴተኛ አዳሪነት ንግድን እና የብልግና ድርጊቶችን ለመዋጋት የጸረ-ሰው ማዘዋወር ልዩ ክፍሎችን በማቋቋም እርምጃውን አጠናክሮ ቀጥሏል።
15 days ago
ሌተና ጄኔራል አልብሩሀን ከዩናይትድ አረብ ኤመሬትስ ጋር ለመነጋገር ፈቃደኛ መሆናቸውን አስታወቁ፡፡
የሱዳን ወታደራዊ መንግስት መሪ የሆኑት ሌተና ጄኔራል አብዱል ፈታህ አልብሩሀን ከዩናይትድ አረብ ኤመሬትስ ጋር ለመነጋገር ፈቃደኝነታቸውን ገልፀው ቅድመ ሁኔታዎችን ግን አስቀምጠዋል፡፡
ጄኔራሉ ከሚድል ኢስት አይ ጋር ባደረጉት ቃለምልልስ ሲናገሩ ‹‹እኛ ከዩናይትድ አረብ ኤመሬትስ ጋር የሰላም ንግግር ለመጀመር ፈቃደኛ ነን፡፡
ይሁንና ይህንን ንግግር ለመጀመር ሱዳን የሱዳን ፍላጎቶች መሟላት ይኖርባቸዋል፡፡
ዩናይትድ አረብ ኤመሬትስ የሱዳንን አንድነት ማክበር ይጠበቅባታል፣ለሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ጦር የምታደርገውን ወታደራዊ ድጋፍ ታቁም ብለዋል፡፡
የጋዜጣው ምንጮች እንደገለፁት ባለፈው ሳምንት አልብሩሀን ወደባህሬን የተጓዙት ባህሬን በሱዳንና በኤመሬትስ መካከል ንግግር እንዲጀመር እያደረገችው ያለው ጥረት አካል ነበር፡፡
በኤመሬትስና በሱዳን መካከል ቀጥተኛ ዲፕሎማሲያዊ መስመር እንዲከፈት የተደረገው ሙከራ እስካሁን ሊሳካ አለመቻሉንም አስታውቋል፡፡
የሱዳን መንግስት ኤመሬትስ ለፈጥኖ ደራሽ ሀይሉ የምትሰጠውን ጦር መሳሪያ ድጋፍ እንድታቋርጥ አቋም መያዙን የገለፀው ዘገባው ቀጥተኛ ንግግር ለማድረግ ይህንን እንደ ቅድመ ሁኔታ ማስቀመጡንም አስረድቷል፡፡
seledadotio
seledadotio
የሱዳን ወታደራዊ መንግስት መሪ የሆኑት ሌተና ጄኔራል አብዱል ፈታህ አልብሩሀን ከዩናይትድ አረብ ኤመሬትስ ጋር ለመነጋገር ፈቃደኝነታቸውን ገልፀው ቅድመ ሁኔታዎችን ግን አስቀምጠዋል፡፡
ጄኔራሉ ከሚድል ኢስት አይ ጋር ባደረጉት ቃለምልልስ ሲናገሩ ‹‹እኛ ከዩናይትድ አረብ ኤመሬትስ ጋር የሰላም ንግግር ለመጀመር ፈቃደኛ ነን፡፡
ይሁንና ይህንን ንግግር ለመጀመር ሱዳን የሱዳን ፍላጎቶች መሟላት ይኖርባቸዋል፡፡
ዩናይትድ አረብ ኤመሬትስ የሱዳንን አንድነት ማክበር ይጠበቅባታል፣ለሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ጦር የምታደርገውን ወታደራዊ ድጋፍ ታቁም ብለዋል፡፡
የጋዜጣው ምንጮች እንደገለፁት ባለፈው ሳምንት አልብሩሀን ወደባህሬን የተጓዙት ባህሬን በሱዳንና በኤመሬትስ መካከል ንግግር እንዲጀመር እያደረገችው ያለው ጥረት አካል ነበር፡፡
በኤመሬትስና በሱዳን መካከል ቀጥተኛ ዲፕሎማሲያዊ መስመር እንዲከፈት የተደረገው ሙከራ እስካሁን ሊሳካ አለመቻሉንም አስታውቋል፡፡
የሱዳን መንግስት ኤመሬትስ ለፈጥኖ ደራሽ ሀይሉ የምትሰጠውን ጦር መሳሪያ ድጋፍ እንድታቋርጥ አቋም መያዙን የገለፀው ዘገባው ቀጥተኛ ንግግር ለማድረግ ይህንን እንደ ቅድመ ሁኔታ ማስቀመጡንም አስረድቷል፡፡
seledadotio
seledadotio
15 days ago
ዶናልድ ትራምፕ በኢራን ቀውስ ምክንያት የልጃቸው ሰርግ ሊያመልጣቸው እንደሚችል ተነገረ
የትራምፕ ትልቁ ልጅ የ48 አመቱ ዶናልድ ትራምፕ ጁኒየር በዚህ ሳምንት መጨረሻ ሞዴል ከሆነችው የ39 አመቷ ቤቲና አንደርሰን ጋር በባሃማስ ጋብቻቸውን ይፈጽማሉ።
ፕሬዝዳንት ትራምፕ በሰርጉ ላይ ለመገኘት ቢፈልጉም፣ በአሁኑ ወቅት ካጋጠማቸው የኢራን ቀውስ አንጻር "የጊዜ አጠባበቁ አመቺ እንዳልሆነ" ለጋዜጠኞች ተናግረዋል።
ለልጇቸው ሰርግ አነስ ያለ ፕሮግራም በዋይት ሃውስ እንደሚያዘጋጁ ግን ተናግረዋል ሲል ብሊክ ጋዜጣ ዘግቧል።
seledadotio
seledadotio
የትራምፕ ትልቁ ልጅ የ48 አመቱ ዶናልድ ትራምፕ ጁኒየር በዚህ ሳምንት መጨረሻ ሞዴል ከሆነችው የ39 አመቷ ቤቲና አንደርሰን ጋር በባሃማስ ጋብቻቸውን ይፈጽማሉ።
ፕሬዝዳንት ትራምፕ በሰርጉ ላይ ለመገኘት ቢፈልጉም፣ በአሁኑ ወቅት ካጋጠማቸው የኢራን ቀውስ አንጻር "የጊዜ አጠባበቁ አመቺ እንዳልሆነ" ለጋዜጠኞች ተናግረዋል።
ለልጇቸው ሰርግ አነስ ያለ ፕሮግራም በዋይት ሃውስ እንደሚያዘጋጁ ግን ተናግረዋል ሲል ብሊክ ጋዜጣ ዘግቧል።
seledadotio
seledadotio
15 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) ወደፈረንሳይ ሊላክ የነበረው ኤርትራዊ እንግሊዝ እስር ቤት ውስጥ ራሱን የማጥፋት ሙከራ አደረገ፡፡ ዘጋርዲያን ጋዜጣ እንደዘገበው ይህ ኤርትራዊ ‹‹ዋን ኢን፣ ዋን አውት›› በተሰኘው ፕሮግራም መሰረት ከእንግሊዝ ተጠርዞ ወደፈረንሳይ እንዲሄድ ትኬት ተቆርጦለት ነበር፡፡ በእንግሊዝ እስር ቤት ውስጥ ተቀምጦ የሚጓዝበትን ቀን በመጠባበቅ ላይ እያለ ግን ራሱን የማጥፋት ሙከራ አድርጓል፡፡
ወደፈረንሳይ ቢሄድ አደጋ እንደሚገጥመው የሰጋው ይህ ኤርትራዊ ራሱን ለማጥፋት እየሞከረ መሆኑን የተናገሩት አብረውት የታሰሩት ሰዎች መሆናቸውን የገለፀው ዘገባው በዚህ የተነሳም የተቆረጠለት የአውሮፕላን ትኬት መሰረዙን አስረድቷል፡፡ በአሁኑ ወቅት በእስር ቤቱ ውስጥ ተመሳሳይ አደጋ በራሱ ላይ እንዳያደርስ በካቴና ታስሮ የቅርብ ክትትል እየተደረገለት ይገኛል፡፡ ይህ ኤርትራዊ ወደፈረንሳይ ተጠርዞ ሊላክ የነበው ባለፈው አመት እንግሊዝና ፈረንሳይ ያደረጉትን ስምምነት ተከትሎ ነው፡፡
በስምምነታቸው መሰረት እንግሊዝ ከፈረንሳይ በጀልባ አቋርጦ እንግሊዝ የገባ አንድ ጥገኝነት ጠያቂን ወደፈረንሳይ ስትልክ ፈረንሳይ ደግሞ በጀልባ የማቋረጥ ሙከራ ያላደረገ አንድ ስደተኛን ወደእንግሊዝ ትልካለች፡፡ በዚህ መሰረትም ባለፉት 8 ወራት 605 ስደተኞች ወደፈረንሳይ ሲላኩ 581 ደግሞ ወደእንግሊዝ ለመግባት ችለዋል፡፡ ሁለቱ አገራት ይህንን ስምምነት ያደረጉት ከፈረንሳይ ወደእንግሊዝ በአነስተኛ ጀልባ የሚደረገውን አደገኛ ጉዞ ለማስቀረት በሚል ነው፡፡ ይሁንና ባለፈው ሳምንት ብቻ በ3 ጀልባዎች 196 ሰዎች ይህንን መንገድ አቋርጠው እንግሊዝ ገብተዋል፡፡
ወደፈረንሳይ ቢሄድ አደጋ እንደሚገጥመው የሰጋው ይህ ኤርትራዊ ራሱን ለማጥፋት እየሞከረ መሆኑን የተናገሩት አብረውት የታሰሩት ሰዎች መሆናቸውን የገለፀው ዘገባው በዚህ የተነሳም የተቆረጠለት የአውሮፕላን ትኬት መሰረዙን አስረድቷል፡፡ በአሁኑ ወቅት በእስር ቤቱ ውስጥ ተመሳሳይ አደጋ በራሱ ላይ እንዳያደርስ በካቴና ታስሮ የቅርብ ክትትል እየተደረገለት ይገኛል፡፡ ይህ ኤርትራዊ ወደፈረንሳይ ተጠርዞ ሊላክ የነበው ባለፈው አመት እንግሊዝና ፈረንሳይ ያደረጉትን ስምምነት ተከትሎ ነው፡፡
በስምምነታቸው መሰረት እንግሊዝ ከፈረንሳይ በጀልባ አቋርጦ እንግሊዝ የገባ አንድ ጥገኝነት ጠያቂን ወደፈረንሳይ ስትልክ ፈረንሳይ ደግሞ በጀልባ የማቋረጥ ሙከራ ያላደረገ አንድ ስደተኛን ወደእንግሊዝ ትልካለች፡፡ በዚህ መሰረትም ባለፉት 8 ወራት 605 ስደተኞች ወደፈረንሳይ ሲላኩ 581 ደግሞ ወደእንግሊዝ ለመግባት ችለዋል፡፡ ሁለቱ አገራት ይህንን ስምምነት ያደረጉት ከፈረንሳይ ወደእንግሊዝ በአነስተኛ ጀልባ የሚደረገውን አደገኛ ጉዞ ለማስቀረት በሚል ነው፡፡ ይሁንና ባለፈው ሳምንት ብቻ በ3 ጀልባዎች 196 ሰዎች ይህንን መንገድ አቋርጠው እንግሊዝ ገብተዋል፡፡
15 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) ሌተና ጄኔራል አልብሩሀን ከዩናይትድ አረብ ኤመሬትስ ጋር ለመነጋገር ፈቃደኛ መሆናቸውን አስታወቁ፡፡ የሱዳን ወታደራዊ መንግስት መሪ የሆኑት ሌተና ጄኔራል አብዱል ፈታህ አልብሩሀን ከዩናይትድ አረብ ኤመሬትስ ጋር ለመነጋገር ፈቃደኝነታቸውን ገልፀው ቅድመ ሁኔታዎችን ግን አስቀምጠዋል፡፡
ጄኔራሉ ከሚድል ኢስት አይ ጋር ባደረጉት ቃለምልልስ ሲናገሩ ‹‹እኛ ከዩናይትድ አረብ ኤመሬትስ ጋር የሰላም ንግግር ለመጀመር ፈቃደኛ ነን፡፡ ይሁንና ይህንን ንግግር ለመጀመር ሱዳን የሱዳን ፍላጎቶች መሟላት ይኖርባቸዋል፡፡ ዩናይትድ አረብ ኤመሬትስ የሱዳንን አንድነት ማክበር ይጠበቅባታል›› ብለዋል፡፡ የጋዜጣው ምንጮች እንደገለፁት ባለፈው ሳምንት አልብሩሀን ወደባህሬን የተጓዙት ባህሬን በሱዳንና በኤመሬትስ መካከል ንግግር እንዲጀመር እያደረገችው ያለው ጥረት አካል ነበር፡፡ በኤመሬትስና በሱዳን መካከል ቀጥተኛ ዲፕሎማሲያዊ መስመር እንዲከፈት የተደረገው ሙከራ እስካሁን ሊሳካ አለመቻሉንም አስታውቋል፡፡ የሱዳን መንግስት ኤመሬትስ ለፈጥኖ ደራሽ ሀይሉ የምትሰጠውን ጦር መሳሪያ ድጋፍ እንድታቋርጥ አቋም መያዙን የገለፀው ዘገባው ቀጥተኛ ንግግር ለማድረግ ይህንን እንደ ቅድመ ሁኔታ ማስቀመጡንም አስረድቷል፡፡
ጄኔራሉ ከሚድል ኢስት አይ ጋር ባደረጉት ቃለምልልስ ሲናገሩ ‹‹እኛ ከዩናይትድ አረብ ኤመሬትስ ጋር የሰላም ንግግር ለመጀመር ፈቃደኛ ነን፡፡ ይሁንና ይህንን ንግግር ለመጀመር ሱዳን የሱዳን ፍላጎቶች መሟላት ይኖርባቸዋል፡፡ ዩናይትድ አረብ ኤመሬትስ የሱዳንን አንድነት ማክበር ይጠበቅባታል›› ብለዋል፡፡ የጋዜጣው ምንጮች እንደገለፁት ባለፈው ሳምንት አልብሩሀን ወደባህሬን የተጓዙት ባህሬን በሱዳንና በኤመሬትስ መካከል ንግግር እንዲጀመር እያደረገችው ያለው ጥረት አካል ነበር፡፡ በኤመሬትስና በሱዳን መካከል ቀጥተኛ ዲፕሎማሲያዊ መስመር እንዲከፈት የተደረገው ሙከራ እስካሁን ሊሳካ አለመቻሉንም አስታውቋል፡፡ የሱዳን መንግስት ኤመሬትስ ለፈጥኖ ደራሽ ሀይሉ የምትሰጠውን ጦር መሳሪያ ድጋፍ እንድታቋርጥ አቋም መያዙን የገለፀው ዘገባው ቀጥተኛ ንግግር ለማድረግ ይህንን እንደ ቅድመ ሁኔታ ማስቀመጡንም አስረድቷል፡፡
Sponsored by
Surafel
15 days ago
የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ሀገር አቀፍ የሰላምና የጸሎት መርሃ ግብር በአዲስ አበባ ሊያካሂድ ነው
የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ሀገር አቀፍ የሰላምና የጸሎት መርሃ ግብር ግንቦት 16 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ አራዳ ፓርክ እንደሚያካሂድ አስታወቀ።
የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ሀገር አቀፍ የሰላምና የጸሎት መርሃ ግብርን አስመልክቶ በዛሬው ዕለት ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቷል።
የጉባኤው ጠቅላይ ጸሐፊ ሊቀ ትጉሃን ቀሲስ ታጋይ ታደለ በመግለጫቸው፣ ሀገር አቀፍ የሰላምና የአብሮነት የጸሎት መርሃ ግብሩ ሁሉም የህብረተሰብ ክፍሎች በጋራ የሚሳተፉበት ነው።
በመርሐ ግብሩ የሰላም እና የአብሮነት መልዕክቶችን ማስተላለፍ፣ የአገሪቱን ብሔራዊ ጥቅም ማስጠበቅ፣እንዲሁም በህዝቦች መካከል ሰላምና አብሮነትን ማጠናከርና ለሀገር መቆም ዋነኛ ትኩረቱ መሆኑን አስገንዝበዋል።
ኅብረተሰቡ በቂ ግንዛቤ በማግኘት በመርሐ ግብሩ ላይ እንዲሳተፍ የመገናኛ ብዙኃን ኋላፊነታቸውን እንዲወጡም ጥሪ አቅርበዋል፡፡
ግንቦት 16 ቀን 2018 ከቀኑ 9፡00 ሰዓት ጀምሮ በሚካሄደው መርሐ ግበር የጋራ እሴቶችና አንድነትን የሚያጎሉ መልዕክቶች እንደሚተላለፉም ጠቅሰዋል፡፡
ለሀገር ዘላቂ ሰላም፣ለሕዝቦች መተሳሰብ እና አብሮነት መጽናት በጋራ ጸሎት እንደሚካሄድም ተናግረዋል፡፡
ጉባኤው ከዚህ ቀደምም በተለያዩ ወቅቶች መሰል ሀገር አቀፍ የጸሎት መርሐ ግብሮችን ሲያካሂድ መቆየቱን አስታውሰዋል፡፡
በዚህ መርሃ ግብር ላይ የሁሉም የጉባኤው አባል ቤተ-እምነት ተቋማት የሃይማኖት መሪዎች፣ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች፣ የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች፣የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ኃላፊዎች እንዲሁም የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች እንደሚሳተፉ ጠቅሰዋል።
#ኢዜአ
የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ሀገር አቀፍ የሰላምና የጸሎት መርሃ ግብር ግንቦት 16 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ አራዳ ፓርክ እንደሚያካሂድ አስታወቀ።
የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ሀገር አቀፍ የሰላምና የጸሎት መርሃ ግብርን አስመልክቶ በዛሬው ዕለት ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቷል።
የጉባኤው ጠቅላይ ጸሐፊ ሊቀ ትጉሃን ቀሲስ ታጋይ ታደለ በመግለጫቸው፣ ሀገር አቀፍ የሰላምና የአብሮነት የጸሎት መርሃ ግብሩ ሁሉም የህብረተሰብ ክፍሎች በጋራ የሚሳተፉበት ነው።
በመርሐ ግብሩ የሰላም እና የአብሮነት መልዕክቶችን ማስተላለፍ፣ የአገሪቱን ብሔራዊ ጥቅም ማስጠበቅ፣እንዲሁም በህዝቦች መካከል ሰላምና አብሮነትን ማጠናከርና ለሀገር መቆም ዋነኛ ትኩረቱ መሆኑን አስገንዝበዋል።
ኅብረተሰቡ በቂ ግንዛቤ በማግኘት በመርሐ ግብሩ ላይ እንዲሳተፍ የመገናኛ ብዙኃን ኋላፊነታቸውን እንዲወጡም ጥሪ አቅርበዋል፡፡
ግንቦት 16 ቀን 2018 ከቀኑ 9፡00 ሰዓት ጀምሮ በሚካሄደው መርሐ ግበር የጋራ እሴቶችና አንድነትን የሚያጎሉ መልዕክቶች እንደሚተላለፉም ጠቅሰዋል፡፡
ለሀገር ዘላቂ ሰላም፣ለሕዝቦች መተሳሰብ እና አብሮነት መጽናት በጋራ ጸሎት እንደሚካሄድም ተናግረዋል፡፡
ጉባኤው ከዚህ ቀደምም በተለያዩ ወቅቶች መሰል ሀገር አቀፍ የጸሎት መርሐ ግብሮችን ሲያካሂድ መቆየቱን አስታውሰዋል፡፡
በዚህ መርሃ ግብር ላይ የሁሉም የጉባኤው አባል ቤተ-እምነት ተቋማት የሃይማኖት መሪዎች፣ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች፣ የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች፣የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ኃላፊዎች እንዲሁም የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች እንደሚሳተፉ ጠቅሰዋል።
#ኢዜአ
16 days ago
(ዘ-ሐበሻ ስፖርት) የእሁዱ የአርሰናል የመጨረሻ ግጥሚያ ትኬት ዋጋ ጣራ ላይ ወጣ፡፡ የፊታችን እሁድ በእንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ አርሰናል ከክሪስታል ፓላስ ጋር ግጥሚያውን ያደርጋል፡፡ በዚህ ጨዋታ ማጠቃለያ ላይ የክለቡ አምበል ማርቲን ኦዲጋርድ ዋንጫውን ሲያነሳ ለማየት የጓጉ የአርሰናል ቀንደኛ ደጋፊዎች ብዙ ናቸው፡፡ ይሁንና ለዚህ በደቡባዊ ለንደን ለሚከናወነው ጨዋታ የተዘጋጀው 25,000 የመግቢያ ትኬት ተሸጦ ካለቀ ሰነባብቷል፡፡
ዘሚረር ጋዜጣ እንደዘገበው የአርሰናል ደጋፊዎች ይህንን ታሪካዊ አጋጣሚ በስታዲየም ተገኝተው ለመመልከት ያላቸውን ፍላጎት ከግምት ውስጥ በማስገባት የዚህ ጨዋታ ትኬት ጣራ ላይ ወጥቷል፡፡ ትኬቶቹ አስቀድመው በማለቃቸው አሁን ለገበያ እየቀረቡ ያሉት የገዙትን ትኬት በሚሸጡ የኦን ላይን ድረገፆች ላይ ብቻ ነው፡፡ እንደዘገባው ፉትቦል ትኬትስ ዶትኮም ላይ የመግቢያ ትኬቱ እስከ 33,000 ፓውንድ ተተምኖለታል፡፡ ይህ ክብር ትሪቢዩን ቦታ ላይ ለመቀመጥ የሚያስችል ትኬት መሆኑንም አስረድቷል፡፡
በሌላ በኩል ቲኮምቦ ዶት ኮም ደግሞ በስታዲየሙ ውስጥ በአርሰናል ደጋፊዎች መቀመጫ ላይ ለሚገኝ ትኬት ከ10,000 ፓውንድ በላይ ዋጋ ማውጣቱንና እየሸጠም እንደሚገኝ ዘገባው ገልጿል፡፡ ለዚህ ለእሁዱ ጨዋታ በድረገፆች ገበያ ርካሽ የሚባለው ትኬት ዋጋ 1300 ፓውንድ መሆኑን የጠቀሰው ዘገባው ይህም በክሪስታን ፓላስ ደጋፊዎች በኩል ለመቀመጥ የሚያስችል ነው ብሏል፡፡
ዘሚረር ጋዜጣ እንደዘገበው የአርሰናል ደጋፊዎች ይህንን ታሪካዊ አጋጣሚ በስታዲየም ተገኝተው ለመመልከት ያላቸውን ፍላጎት ከግምት ውስጥ በማስገባት የዚህ ጨዋታ ትኬት ጣራ ላይ ወጥቷል፡፡ ትኬቶቹ አስቀድመው በማለቃቸው አሁን ለገበያ እየቀረቡ ያሉት የገዙትን ትኬት በሚሸጡ የኦን ላይን ድረገፆች ላይ ብቻ ነው፡፡ እንደዘገባው ፉትቦል ትኬትስ ዶትኮም ላይ የመግቢያ ትኬቱ እስከ 33,000 ፓውንድ ተተምኖለታል፡፡ ይህ ክብር ትሪቢዩን ቦታ ላይ ለመቀመጥ የሚያስችል ትኬት መሆኑንም አስረድቷል፡፡
በሌላ በኩል ቲኮምቦ ዶት ኮም ደግሞ በስታዲየሙ ውስጥ በአርሰናል ደጋፊዎች መቀመጫ ላይ ለሚገኝ ትኬት ከ10,000 ፓውንድ በላይ ዋጋ ማውጣቱንና እየሸጠም እንደሚገኝ ዘገባው ገልጿል፡፡ ለዚህ ለእሁዱ ጨዋታ በድረገፆች ገበያ ርካሽ የሚባለው ትኬት ዋጋ 1300 ፓውንድ መሆኑን የጠቀሰው ዘገባው ይህም በክሪስታን ፓላስ ደጋፊዎች በኩል ለመቀመጥ የሚያስችል ነው ብሏል፡፡
16 days ago
ቶሚ ፊትነስ ሴንተር ለአገራችን አዲስ የሆነውን “ፒላቲዝ” ስፖርት ስቱዲዮ በይፋ ከፈተ!
#fastmereja I በኢትዮጵያ የፊትነስ ዘርፍ በርካታ ስራዎችን በመስራት የሚታወቀው ቶሚ ፊትነስ ሴንተር፣ በመላው ዓለም ከፍተኛ ተወዳጅነትና ውጤታማነትን ያስመዘገበውን፣ ለአገራችን ደግሞ አዲስ የሆነውን “ፒላቲዝ” (Pilates) ስፖርት ስቱዲዮ በቦሌ ዮድ አቢሲኒያ አካባቢ በይፋ መክፈቱን አስታወቀ።
የድርጅቱ መስራችና ባለቤት አቶ ቶማስ ሀይሉ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ እንደተናገሩት፣ ማዕከሉ ለአገራችን አዲስ የሆኑ የሰውነት ማጠናከሪያ፣ የአቋም ማስተካከያና ከጉዳት ማገገሚያ ዘመናዊ የስፖርት አይነቶችን ይዞ መቅረቡን ገልጿል።
አቶ ቶማስ ሀይሉ አክለውም፣ ይህ አዲስ ስቱዲዮ በውጭ ሀገር ከፍተኛ ልምድና እውቀት ያላቸውን ፕሮፌሽናል አሰልጣኞች ያካተተ መሆኑን ገልጸው፣ የሚሰጡት አገልግሎቶች እጅግ ዘመናዊና የቅንጦት (Luxury) ቢሆኑም፣ የተቀረጸው የዋጋ ተመን ግን የህብረተሰቡን አቅም ያገናዘበና ተመጣጣኝ (Affordable) መሆኑን አስረድተዋል።
ይህ የስፖርት አይነት እንቅስቃሴዎችን በጥንቃቄ በመቆጣጠር የሰውነት ጥንካሬን፣ የመተጣጠፍ ብቃትን፣ የፖስቸር(የአቋም) መስተካከልን እና ትክክለኛ አተነፋፈስን ለማሳደግ ታስቦ የተዘጋጀ ነው።
አዲሱ ስቱዲዮ የሆድና የጀርባ ጡንቻዎችን ለማዳበር፣ የሰውነት ቅርጽን ለማስተካከል እንዲሁም ከጀርባ ህመም፣ ከቀዶ ጥገና እና ከመገጣጠሚያ ጉዳቶች በፍጥነት ለማገገም የሚረዱ ዘመናዊ አገልግሎቶችን ያካተተ መሆኑ ነዉ የተገለፀዉ።
ስቱዲዮው ከሚሰጣቸው ልዩ ልዩ አገልግሎቶች መካከል "ሪፎርመር" የተባለውን አልጋ መሰል ማሽን በመጠቀም ሁሉንም የሰውነት ክፍሎች የሚያሰራው ሪፎርመር ፒላቲስ፣ ከ35 እስከ 40 ዲግሪ ሴንቲግሬድ በሆነ ሙቀት ባለው ክፍል ውስጥ የሚሰራው "ሆት ፒላቲስ"፣ አፍሪካን መሰረት ያደረገውና ለውጥረት መቀነሻ የሚጠቅመው "ኬሜቲክዮጋ" እንዲሁም ለነፍሰጡር እናቶች ተብሎ የተዘጋጀው "የነፍሰጡር ዮጋ (Prenatal Yoga)" ዋና ዋናዎቹ ናቸው፡፡
ማዕከሉ መደበኛና ሙሉ ሥራውን ከመጪው ሰኞ ጀምሮ በይፋ የሚጀምር በመሆኑ፣ ፍላጎት ያላቸው ደንበኞች በቦታ እጥረት እንዳይቸገሩ ቀድመው መመዝገብና ቦታ መያዝ እንደሚችሉ ጥሪ ቀርቧል።
#fastmereja I በኢትዮጵያ የፊትነስ ዘርፍ በርካታ ስራዎችን በመስራት የሚታወቀው ቶሚ ፊትነስ ሴንተር፣ በመላው ዓለም ከፍተኛ ተወዳጅነትና ውጤታማነትን ያስመዘገበውን፣ ለአገራችን ደግሞ አዲስ የሆነውን “ፒላቲዝ” (Pilates) ስፖርት ስቱዲዮ በቦሌ ዮድ አቢሲኒያ አካባቢ በይፋ መክፈቱን አስታወቀ።
የድርጅቱ መስራችና ባለቤት አቶ ቶማስ ሀይሉ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ እንደተናገሩት፣ ማዕከሉ ለአገራችን አዲስ የሆኑ የሰውነት ማጠናከሪያ፣ የአቋም ማስተካከያና ከጉዳት ማገገሚያ ዘመናዊ የስፖርት አይነቶችን ይዞ መቅረቡን ገልጿል።
አቶ ቶማስ ሀይሉ አክለውም፣ ይህ አዲስ ስቱዲዮ በውጭ ሀገር ከፍተኛ ልምድና እውቀት ያላቸውን ፕሮፌሽናል አሰልጣኞች ያካተተ መሆኑን ገልጸው፣ የሚሰጡት አገልግሎቶች እጅግ ዘመናዊና የቅንጦት (Luxury) ቢሆኑም፣ የተቀረጸው የዋጋ ተመን ግን የህብረተሰቡን አቅም ያገናዘበና ተመጣጣኝ (Affordable) መሆኑን አስረድተዋል።
ይህ የስፖርት አይነት እንቅስቃሴዎችን በጥንቃቄ በመቆጣጠር የሰውነት ጥንካሬን፣ የመተጣጠፍ ብቃትን፣ የፖስቸር(የአቋም) መስተካከልን እና ትክክለኛ አተነፋፈስን ለማሳደግ ታስቦ የተዘጋጀ ነው።
አዲሱ ስቱዲዮ የሆድና የጀርባ ጡንቻዎችን ለማዳበር፣ የሰውነት ቅርጽን ለማስተካከል እንዲሁም ከጀርባ ህመም፣ ከቀዶ ጥገና እና ከመገጣጠሚያ ጉዳቶች በፍጥነት ለማገገም የሚረዱ ዘመናዊ አገልግሎቶችን ያካተተ መሆኑ ነዉ የተገለፀዉ።
ስቱዲዮው ከሚሰጣቸው ልዩ ልዩ አገልግሎቶች መካከል "ሪፎርመር" የተባለውን አልጋ መሰል ማሽን በመጠቀም ሁሉንም የሰውነት ክፍሎች የሚያሰራው ሪፎርመር ፒላቲስ፣ ከ35 እስከ 40 ዲግሪ ሴንቲግሬድ በሆነ ሙቀት ባለው ክፍል ውስጥ የሚሰራው "ሆት ፒላቲስ"፣ አፍሪካን መሰረት ያደረገውና ለውጥረት መቀነሻ የሚጠቅመው "ኬሜቲክዮጋ" እንዲሁም ለነፍሰጡር እናቶች ተብሎ የተዘጋጀው "የነፍሰጡር ዮጋ (Prenatal Yoga)" ዋና ዋናዎቹ ናቸው፡፡
ማዕከሉ መደበኛና ሙሉ ሥራውን ከመጪው ሰኞ ጀምሮ በይፋ የሚጀምር በመሆኑ፣ ፍላጎት ያላቸው ደንበኞች በቦታ እጥረት እንዳይቸገሩ ቀድመው መመዝገብና ቦታ መያዝ እንደሚችሉ ጥሪ ቀርቧል።
17 days ago
''ማንቺስተር ያሸነፈ ቀን !''
ትናንት አርሰናል አሸነፈ! በህይወቱ ሙሉ ሲመኘው የነበረውን ይህን ድል ቆሞ ማየት የነበረበት አንድ ሰዉ ነበር።
ብዙ ጊዜ ማንቺስተር አሸንፎ ደጋፊዎቹ መሬት አልበቃቸው ብሎ ሳይ እንደሁሌውም ትዝያለኝ ያ ራሱን 'የአርሰናል ቁልፍ ሰው' አድርጎ ይቆጥር የነበረው ታናሽ ወንድሜ ነው
በፍቃዱ ብርሃኑ ይባላል… እማዬ “ፍቃዴ” ትለው ነበር፡፡ እኔን ጨምሮ እሱን የሚያውቁት ሁሉ “ፍቄ” ብለው ነበር የሚጠሩት፡፡ በህጻን አዛውንቱ ተወዳጅ የነበረ ወንድሜ .... ዛሬ በህይወት የለም።
ፍቄ ሁሌም ማታ የጠንቋይ መጣፍ የመሰለ ደቃቅ ጽሁፍ የታጨቀበትን ሊብሮ ጋዜጣ ይዞ ወደቤት ይመጣል። ገና ጎረምሳ ነው፡፡ ረጅም ...1 ሜትር ከ87 ሳ.ሜ ቁመቱን በአሮጌው ሶፋ ላይ ዧ አድርጎ እንሩን አንፈራጦ ይቀመጥና …. ፊቱን ጋዜጣው ውስጥ ቀብሮ …ኮስተር ፈታ እያለ ‘የነቡናን እና የነአርሴን' ወግ ይጨመጭማል።
“… ምንድነው ግን የምታነበው?” ትለዋለች እማዬ፡፡ ”ስፖርት ነው እማ.. ብዙም አታውቂውም” ይላታል።
”ኡኡቴ! አዋቂ ነኝ ብለህ ሞተሃል..ደሞ ለቅሪላ ወሬ!” ትላለች።
” ጭንቅላትህን በኳስ ዕወቀት ከምትሞላ ትምህርትህ ላይ አትበረታም ነበር? …ደደብ!! …ነገ አርሰናል መጥቶ ይፈተንልህ መሰለህ? ..” ብዬ ልጮህበት እፈልጋለሁ።
ግን ብዙ ጊዜ ይህንን ብዬው ጉሮሮዬን አመመኝ እንጂ ያመጣሁት ለውጥ የለም።
እማዬ ማለዳ ወደቤተክርስቲያን በምትሄድባቸው ቀናት ወደእግዜር ከምትወስደው የራሷ ጥያቄዎች በተጨማሪ ፍቄ የሚያዛት ተጨማሪ ፀሎት አለ። ጨዋታ ያለ ቀን ወይ ቡና… ወይ አርሰናል እንዲያሸንፍ እንድትጸልይለት ይነግራታል፡፡
የሆነ ጊዜ የቡና ረከቦቷን የምትሸፍንበትን ጨርቅ አነስቶ ጥሎ በምትኩ ሁለት የቡና አርማ ያለበትን ባንዲራ አሰርቶ አመጣና አንዱን “የቡና ስኒ በቡና አርማ ነው መሸፈን ያለበት” ብሎ ሰጣት፡፡ አንዱን ደግሞ የቤታችን ግድግዳ ላይ በሚስማር መትቶ ሰቀለው፡፡ ቤት ስገባና የሆነውን ሳይ ተናደድኩና ገንጥዬ ጣልኩበት፡፡ የረከቦቱን ግን እማዬ ከለከለችኝ፡፡ "ይሁን፣በገዛ ሲኒዬ ምን አገባህ" ብላ ፡፡ እነዚያ ጨርቆች ዛሬም ድረስ ቤታችን አሉ፡፡
እማዬን “ እሙ!” ነበር የሚላት፡፡ የሚተኛው ከሷ ጋር ነው፡፡ የመጨረሻ ልጅ ስለሆነ ነው መሰለኝ እንደነፍሷ ትወደዋለች፡፡ ጨዋታ ያለ ቀን ታዲያ እማዬ ማለዳ ወደቤተክርስቲያን ለመሄድ ስትነሳ የተሸፈነበትን ብርድልብስ ገለጥ ያደርግና “እሙ! ዛሬ የኔ ቡድን ይጫወታል።እንዲያሸንፍ ጸልዪልኝ ...ካሸነፍን ስለት ታስገቢልኛለሽ! ” ይላታል፡፡
“አይ እዳዬ!..... ደሞ ዛሬ አቡነ ተክለሃይማኖት እንዴት ያረጉኝ ይሆን” ትላለች ። እማዬ ስትምልም ስትለምንም በአቡነ ተክለሃይማኖት ነው፡፡
አንድ ቀን 'የምር ስለሱ ኳስ ጨዋታ ትጸልያለሽ?' ብዬ ጠየቅኳት፡፡ “እንዴ አዎና!...ተክልዬ !! የዚህን ልጅ ልብ የበሉት ባለኳሶች እንዲያሸንፉ እርዱልኝ…..ጉድ እንዳይሰሩኝ ኋላ! እላቸዋለሁ” አለችና አሳቀችኝ።
ምን ታድርግ? የርሱ ክለብ የተሸነፈ’ለታ ቤታችን የሚፈጠረውን ነገር ስለማውቅ አልፈረድኩባትም፡፡
ጨዋታ ያለ ቀን ገና በጠዋቱ አጠገቤ ቆም ይልና…”መላ’ዬ …ጨዋታው 3 ከ 45 ይጀምራል። ከዚያ በፊት ሃይላይት አለ። ወደ አምስት ሰዓት አካባቢ ያልቃል። እንደጨረስኩ ወዲያው እመጣለሁ።” ይላል።
ማስፈቀዱ ነው፡፡ ዝም እላለሁ።ቆሞ ያየኛል።ዝም እላለሁ። አይሄድም፡፡ እኔ ጥዬው እሄዳለሁ።
አንዳንዴ የሆነ ልቡን ስልብ አድርጎ ራሱን የሚያስተው ነገር አለ፡፡ ሲጨነቅ ወይም ሲበሳጭ እንዲያ ይሆናል፡፡
አርሰናል የተሸነፈ’ለት ታዲያ ብዙ ጊዜ ያ ህመም ይነሳበታል፡፡ ቤት እንደገባ በዚያ ቁመቱ ሶፋ ላይ ዧ ብሎ ይወድቃል፡፡ ጸጥ ነው የሚለው፡፡ አንዳንዴ ሞተ ብለን የምንጮህበት ቀን አለ።ውሃም ጸበልም ደፋፍተንበት ነፍስ ከዘራ በኋላ “ደህና ነኝ እኮ” ሲል ደግሞ የኔ ንዴት በተራው አናቴ ላይ ይወጣል።
“አንተ በማይረባ ኳስ እየመጣህ ትዘረጋለህና እኛ መጨነቅ አለብን?” ብዬ እጮህበታለሁ፡፡ መልስ አይሰጠኝም፡፡ሌላ ቀንም እንዲሁ ይሆናል፡፡
የሆኑ ከሌላ ሰፈር የሚመጡ የጊዮርጊስ ይሁኑ የማንቺስተር ደጋፊዎች እሱን ሁሌም እንደተቃረኑት ነበር። ኳስ የሚያዩት አብረው መሰለኝ ፡፡
ጨዋታ ያለ ቀን ታዲያ...ብዙ ጊዜ እኩለ ሌሊት ከእንቅልፌ የሚያባንነኝ በራችን አቅራቢያ የምሰማው የብዙ ልጆች ዘፈን የሚመስል ጫጫታ ነበር። እኛ ቤት በር ላይ አርሰናልን የሚሳደብ ዘፈን ከሰማሁ በቃ ነገር አለ ማለት ነው !።
ፍቄን ለማብሸቅ የሚዘፈን ዘፈን መሆኑን አውቃለሁ።
ልጆቹ የሚሉት ነገር አይገባኝም። ግን ሁለቱ ቡድኖች ከማንም ጋር ይጫወቱ ብቻ አርሰናል ከተሸነፈ ወይም ማንቺስተር ካሸነፈ እሱን ለማብሸቅ እኩለ ሌሊት በራችን ላይ ይመጡና ይጨፍራሉ።
አንድ ቀን ከነሱ ጋር ሲደባደብ ፖሊሶች ደረሱና ብዙዎቹን ያዟቸው፡፡ እሱንም ይዘውት መኪና ላይ ከጫኑት በኋላ የኔ ወንድም መሆኑን ሲነግራቸው ደውለው ጠርተውኝ ፊቴ የመጨረሻ ማስጠንቀቂያ ሰጥተው ለቀቁት፡፡ ለእማዬ ብዬ እንጂ እስር ቤትን ትንሽ ቢቀምሳት ቅር አይለኝም ነበር፡፡
እሱ የሚደግፈው ቡድን ያሸነፈ’ለት ደግሞ ታሪክ ይገለበጣል፡፡እማዬ ይህንን ስትሰማ ወደሰማይ እያንጋጠጠች “ዛሬስ ተክለሃይማኖት ገላገሉኝ !” ትላለች።
የዚያን ቀን ታዲያ ሌሊቱን ሙሉ እንቅልፍ አይወስደውም። ብቻውን ይስቃል። አልጋው ራስጌ ፎቷቸውን የሰቀለውን ማንነታቸውን የማላውቃቸውን ተጨዋቾች በተኛበት አንጋጦ ያያቸዋል፡፡ ጸጥ ባለው ሌሊት ድንገት ይነሳና “ይሄ የተረገመ ልጅ! ሰራላቸው እኮ!” ብሎ በሳቅ ፍርስ ይላል።
አንዳንዴ ዝም ብዬ ሳየው ጤነኛ ሁሉ አይመስለኝም ነበር ።እማዬ ግን “ተወው ልጅ አይደል? ብቻ አይመመው እንጂ ሲለፈልፍ ቢያድር እኔ ምን ቸገረኝ…ሲያድግ ይተወዋል” ትላለች፡፡
ፍቄ ገና በ21 ዓመቱ አንድ እሁድ ቀን ድንገት ራሱን ስቶ ወደቀ፡፡ ሆስፒታል በገባ በሶስተኛ ቀኑ …እኛንም የሚወዳቸውን ቡናና አርሰናልንም ሳይሰናበት በዚያው ሄደ።
የቀብሩ ዕለት የነበረው ህዝብ ብዛት እስካሁን ሳስበውም ይገርመኛል። በዚያ እድሜው ትምህርቱን ትቶ በሚሰራው ስራ የሚያገኘውን ደመወዝ ሁሉ የሰፈር አቅመደካሞችን ፣ ልጅ ያላቸው የኔ ቢጤዎችን ወዘተ በቋሚነት ይረዳበት እንደነበር ያወቅኩት የለቅሶው ሰሞን ሰዎች ስለርሱ ሲያወሩ በሰማኋቸው ታሪኮች ነው፡፡
በስሙ ትልቅ የእግር ኳስ ግጥሚያ ተዘጋጅቶለትም ነበር፡፡ የዋንጫው ቀን አሸናፊውን ቡድን ስሸልም ስሜቴን መቆጣጠር አቅቶኝ ነበር ፡፡
አሁንም ታዲያ ኳስ በሚታይባቸው ቤቶች በኩል ሳልፍ የደጋፊዎችን ጩኸት ስሰማ ፊቴ ላይ ድቅን የሚልብኝ አሱ ነው ። ምን ያደርጋል ያንን ምድር የማይበቃው የሚመስል ዋልያ …ያች ቀዝቃዛ ቀን እንደዋዛ ይዛው ሄደች....የርሱ መጉደል በቤታችን ይዞት የመጣው ከባድ ሃዘን እናቴን ህመምተኛ አድርጓት ኖሯል፡፡ ባሰብኩት ቁጥር የሚናፍቀኝ ከፊቱ የማይጠፋው ፈገግታ ነው፡፡
ፍቄ ወንድሜ ! ….ነፍስህ በሰላም ትረፍ !!
የሚናፍቅህ ወንድምህ
መላኩ ብርሃኑ
ትናንት አርሰናል አሸነፈ! በህይወቱ ሙሉ ሲመኘው የነበረውን ይህን ድል ቆሞ ማየት የነበረበት አንድ ሰዉ ነበር።
ብዙ ጊዜ ማንቺስተር አሸንፎ ደጋፊዎቹ መሬት አልበቃቸው ብሎ ሳይ እንደሁሌውም ትዝያለኝ ያ ራሱን 'የአርሰናል ቁልፍ ሰው' አድርጎ ይቆጥር የነበረው ታናሽ ወንድሜ ነው
በፍቃዱ ብርሃኑ ይባላል… እማዬ “ፍቃዴ” ትለው ነበር፡፡ እኔን ጨምሮ እሱን የሚያውቁት ሁሉ “ፍቄ” ብለው ነበር የሚጠሩት፡፡ በህጻን አዛውንቱ ተወዳጅ የነበረ ወንድሜ .... ዛሬ በህይወት የለም።
ፍቄ ሁሌም ማታ የጠንቋይ መጣፍ የመሰለ ደቃቅ ጽሁፍ የታጨቀበትን ሊብሮ ጋዜጣ ይዞ ወደቤት ይመጣል። ገና ጎረምሳ ነው፡፡ ረጅም ...1 ሜትር ከ87 ሳ.ሜ ቁመቱን በአሮጌው ሶፋ ላይ ዧ አድርጎ እንሩን አንፈራጦ ይቀመጥና …. ፊቱን ጋዜጣው ውስጥ ቀብሮ …ኮስተር ፈታ እያለ ‘የነቡናን እና የነአርሴን' ወግ ይጨመጭማል።
“… ምንድነው ግን የምታነበው?” ትለዋለች እማዬ፡፡ ”ስፖርት ነው እማ.. ብዙም አታውቂውም” ይላታል።
”ኡኡቴ! አዋቂ ነኝ ብለህ ሞተሃል..ደሞ ለቅሪላ ወሬ!” ትላለች።
” ጭንቅላትህን በኳስ ዕወቀት ከምትሞላ ትምህርትህ ላይ አትበረታም ነበር? …ደደብ!! …ነገ አርሰናል መጥቶ ይፈተንልህ መሰለህ? ..” ብዬ ልጮህበት እፈልጋለሁ።
ግን ብዙ ጊዜ ይህንን ብዬው ጉሮሮዬን አመመኝ እንጂ ያመጣሁት ለውጥ የለም።
እማዬ ማለዳ ወደቤተክርስቲያን በምትሄድባቸው ቀናት ወደእግዜር ከምትወስደው የራሷ ጥያቄዎች በተጨማሪ ፍቄ የሚያዛት ተጨማሪ ፀሎት አለ። ጨዋታ ያለ ቀን ወይ ቡና… ወይ አርሰናል እንዲያሸንፍ እንድትጸልይለት ይነግራታል፡፡
የሆነ ጊዜ የቡና ረከቦቷን የምትሸፍንበትን ጨርቅ አነስቶ ጥሎ በምትኩ ሁለት የቡና አርማ ያለበትን ባንዲራ አሰርቶ አመጣና አንዱን “የቡና ስኒ በቡና አርማ ነው መሸፈን ያለበት” ብሎ ሰጣት፡፡ አንዱን ደግሞ የቤታችን ግድግዳ ላይ በሚስማር መትቶ ሰቀለው፡፡ ቤት ስገባና የሆነውን ሳይ ተናደድኩና ገንጥዬ ጣልኩበት፡፡ የረከቦቱን ግን እማዬ ከለከለችኝ፡፡ "ይሁን፣በገዛ ሲኒዬ ምን አገባህ" ብላ ፡፡ እነዚያ ጨርቆች ዛሬም ድረስ ቤታችን አሉ፡፡
እማዬን “ እሙ!” ነበር የሚላት፡፡ የሚተኛው ከሷ ጋር ነው፡፡ የመጨረሻ ልጅ ስለሆነ ነው መሰለኝ እንደነፍሷ ትወደዋለች፡፡ ጨዋታ ያለ ቀን ታዲያ እማዬ ማለዳ ወደቤተክርስቲያን ለመሄድ ስትነሳ የተሸፈነበትን ብርድልብስ ገለጥ ያደርግና “እሙ! ዛሬ የኔ ቡድን ይጫወታል።እንዲያሸንፍ ጸልዪልኝ ...ካሸነፍን ስለት ታስገቢልኛለሽ! ” ይላታል፡፡
“አይ እዳዬ!..... ደሞ ዛሬ አቡነ ተክለሃይማኖት እንዴት ያረጉኝ ይሆን” ትላለች ። እማዬ ስትምልም ስትለምንም በአቡነ ተክለሃይማኖት ነው፡፡
አንድ ቀን 'የምር ስለሱ ኳስ ጨዋታ ትጸልያለሽ?' ብዬ ጠየቅኳት፡፡ “እንዴ አዎና!...ተክልዬ !! የዚህን ልጅ ልብ የበሉት ባለኳሶች እንዲያሸንፉ እርዱልኝ…..ጉድ እንዳይሰሩኝ ኋላ! እላቸዋለሁ” አለችና አሳቀችኝ።
ምን ታድርግ? የርሱ ክለብ የተሸነፈ’ለታ ቤታችን የሚፈጠረውን ነገር ስለማውቅ አልፈረድኩባትም፡፡
ጨዋታ ያለ ቀን ገና በጠዋቱ አጠገቤ ቆም ይልና…”መላ’ዬ …ጨዋታው 3 ከ 45 ይጀምራል። ከዚያ በፊት ሃይላይት አለ። ወደ አምስት ሰዓት አካባቢ ያልቃል። እንደጨረስኩ ወዲያው እመጣለሁ።” ይላል።
ማስፈቀዱ ነው፡፡ ዝም እላለሁ።ቆሞ ያየኛል።ዝም እላለሁ። አይሄድም፡፡ እኔ ጥዬው እሄዳለሁ።
አንዳንዴ የሆነ ልቡን ስልብ አድርጎ ራሱን የሚያስተው ነገር አለ፡፡ ሲጨነቅ ወይም ሲበሳጭ እንዲያ ይሆናል፡፡
አርሰናል የተሸነፈ’ለት ታዲያ ብዙ ጊዜ ያ ህመም ይነሳበታል፡፡ ቤት እንደገባ በዚያ ቁመቱ ሶፋ ላይ ዧ ብሎ ይወድቃል፡፡ ጸጥ ነው የሚለው፡፡ አንዳንዴ ሞተ ብለን የምንጮህበት ቀን አለ።ውሃም ጸበልም ደፋፍተንበት ነፍስ ከዘራ በኋላ “ደህና ነኝ እኮ” ሲል ደግሞ የኔ ንዴት በተራው አናቴ ላይ ይወጣል።
“አንተ በማይረባ ኳስ እየመጣህ ትዘረጋለህና እኛ መጨነቅ አለብን?” ብዬ እጮህበታለሁ፡፡ መልስ አይሰጠኝም፡፡ሌላ ቀንም እንዲሁ ይሆናል፡፡
የሆኑ ከሌላ ሰፈር የሚመጡ የጊዮርጊስ ይሁኑ የማንቺስተር ደጋፊዎች እሱን ሁሌም እንደተቃረኑት ነበር። ኳስ የሚያዩት አብረው መሰለኝ ፡፡
ጨዋታ ያለ ቀን ታዲያ...ብዙ ጊዜ እኩለ ሌሊት ከእንቅልፌ የሚያባንነኝ በራችን አቅራቢያ የምሰማው የብዙ ልጆች ዘፈን የሚመስል ጫጫታ ነበር። እኛ ቤት በር ላይ አርሰናልን የሚሳደብ ዘፈን ከሰማሁ በቃ ነገር አለ ማለት ነው !።
ፍቄን ለማብሸቅ የሚዘፈን ዘፈን መሆኑን አውቃለሁ።
ልጆቹ የሚሉት ነገር አይገባኝም። ግን ሁለቱ ቡድኖች ከማንም ጋር ይጫወቱ ብቻ አርሰናል ከተሸነፈ ወይም ማንቺስተር ካሸነፈ እሱን ለማብሸቅ እኩለ ሌሊት በራችን ላይ ይመጡና ይጨፍራሉ።
አንድ ቀን ከነሱ ጋር ሲደባደብ ፖሊሶች ደረሱና ብዙዎቹን ያዟቸው፡፡ እሱንም ይዘውት መኪና ላይ ከጫኑት በኋላ የኔ ወንድም መሆኑን ሲነግራቸው ደውለው ጠርተውኝ ፊቴ የመጨረሻ ማስጠንቀቂያ ሰጥተው ለቀቁት፡፡ ለእማዬ ብዬ እንጂ እስር ቤትን ትንሽ ቢቀምሳት ቅር አይለኝም ነበር፡፡
እሱ የሚደግፈው ቡድን ያሸነፈ’ለት ደግሞ ታሪክ ይገለበጣል፡፡እማዬ ይህንን ስትሰማ ወደሰማይ እያንጋጠጠች “ዛሬስ ተክለሃይማኖት ገላገሉኝ !” ትላለች።
የዚያን ቀን ታዲያ ሌሊቱን ሙሉ እንቅልፍ አይወስደውም። ብቻውን ይስቃል። አልጋው ራስጌ ፎቷቸውን የሰቀለውን ማንነታቸውን የማላውቃቸውን ተጨዋቾች በተኛበት አንጋጦ ያያቸዋል፡፡ ጸጥ ባለው ሌሊት ድንገት ይነሳና “ይሄ የተረገመ ልጅ! ሰራላቸው እኮ!” ብሎ በሳቅ ፍርስ ይላል።
አንዳንዴ ዝም ብዬ ሳየው ጤነኛ ሁሉ አይመስለኝም ነበር ።እማዬ ግን “ተወው ልጅ አይደል? ብቻ አይመመው እንጂ ሲለፈልፍ ቢያድር እኔ ምን ቸገረኝ…ሲያድግ ይተወዋል” ትላለች፡፡
ፍቄ ገና በ21 ዓመቱ አንድ እሁድ ቀን ድንገት ራሱን ስቶ ወደቀ፡፡ ሆስፒታል በገባ በሶስተኛ ቀኑ …እኛንም የሚወዳቸውን ቡናና አርሰናልንም ሳይሰናበት በዚያው ሄደ።
የቀብሩ ዕለት የነበረው ህዝብ ብዛት እስካሁን ሳስበውም ይገርመኛል። በዚያ እድሜው ትምህርቱን ትቶ በሚሰራው ስራ የሚያገኘውን ደመወዝ ሁሉ የሰፈር አቅመደካሞችን ፣ ልጅ ያላቸው የኔ ቢጤዎችን ወዘተ በቋሚነት ይረዳበት እንደነበር ያወቅኩት የለቅሶው ሰሞን ሰዎች ስለርሱ ሲያወሩ በሰማኋቸው ታሪኮች ነው፡፡
በስሙ ትልቅ የእግር ኳስ ግጥሚያ ተዘጋጅቶለትም ነበር፡፡ የዋንጫው ቀን አሸናፊውን ቡድን ስሸልም ስሜቴን መቆጣጠር አቅቶኝ ነበር ፡፡
አሁንም ታዲያ ኳስ በሚታይባቸው ቤቶች በኩል ሳልፍ የደጋፊዎችን ጩኸት ስሰማ ፊቴ ላይ ድቅን የሚልብኝ አሱ ነው ። ምን ያደርጋል ያንን ምድር የማይበቃው የሚመስል ዋልያ …ያች ቀዝቃዛ ቀን እንደዋዛ ይዛው ሄደች....የርሱ መጉደል በቤታችን ይዞት የመጣው ከባድ ሃዘን እናቴን ህመምተኛ አድርጓት ኖሯል፡፡ ባሰብኩት ቁጥር የሚናፍቀኝ ከፊቱ የማይጠፋው ፈገግታ ነው፡፡
ፍቄ ወንድሜ ! ….ነፍስህ በሰላም ትረፍ !!
የሚናፍቅህ ወንድምህ
መላኩ ብርሃኑ
17 days ago
«ወደ ሥልጣን እንዲመለስ ከተባለዉ ዉሳኔ ጀርባ ያሉት ከ 100 የማይበልጡ ናቸዉ» ሳሞራ ዩኑስ
የቀድሞው የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ኢታማዦር ሹም ጄኔራል ሳሞራ ዩኑስ በትግራይ ክልል ህወሓትን ወደ ስልጣን ለመመለስ የተደረገዉን ውሳኔ አጥብቀዉ ተቃወሙ። በዚህ ሳምንት ከውጋሕት ጋዜጣ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ "የቀድሞ አመራሮች እና ምክር ቤት (በትግራይ) ወደነበሩበት እንዲመለሱ መወሰኑ ህዝቡን ከልክ በላይ ጭንቀት ውስጥ ከቶታል „ብለዋል። ሳሞራ የህወሓት ነባር ታጋይና አባልም ነበሩ።
ሳሞራ አክለውም የትግራይ ህዝብ የህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) የግል ንብረት ስላልሆነ በፓርቲው ታግቶ መቀመጥ የለበትም ሲሉም አክለዋል። ከጦርነቱ በፊት የነበረው የክልል ምክር ቤትና አስተዳደር «ወደ ሥልጣን እንዲመለስ ከተባለዉ ዉሳኔ ጀርባ ያሉት ከ 100 የማይበልጡ ናቸዉ፣ ውሳኔዉን ያሳለፉትም ከተጠያቂነት ለመዳን ያሰበ ዓላማን የያዘ ነዉ» ብለዉ እንደሚያስቡ ሳሞራ ዩንስ ተናግረዋል።
DW Amharic
የቀድሞው የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ኢታማዦር ሹም ጄኔራል ሳሞራ ዩኑስ በትግራይ ክልል ህወሓትን ወደ ስልጣን ለመመለስ የተደረገዉን ውሳኔ አጥብቀዉ ተቃወሙ። በዚህ ሳምንት ከውጋሕት ጋዜጣ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ "የቀድሞ አመራሮች እና ምክር ቤት (በትግራይ) ወደነበሩበት እንዲመለሱ መወሰኑ ህዝቡን ከልክ በላይ ጭንቀት ውስጥ ከቶታል „ብለዋል። ሳሞራ የህወሓት ነባር ታጋይና አባልም ነበሩ።
ሳሞራ አክለውም የትግራይ ህዝብ የህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) የግል ንብረት ስላልሆነ በፓርቲው ታግቶ መቀመጥ የለበትም ሲሉም አክለዋል። ከጦርነቱ በፊት የነበረው የክልል ምክር ቤትና አስተዳደር «ወደ ሥልጣን እንዲመለስ ከተባለዉ ዉሳኔ ጀርባ ያሉት ከ 100 የማይበልጡ ናቸዉ፣ ውሳኔዉን ያሳለፉትም ከተጠያቂነት ለመዳን ያሰበ ዓላማን የያዘ ነዉ» ብለዉ እንደሚያስቡ ሳሞራ ዩንስ ተናግረዋል።
DW Amharic
Comments