51 mins. ago
የየካ ደብረ ሣህል ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን የሚያሰራውን ቤተሰሊሆም አጠቃላይ ሆስፒታል ህንፃ ግንባታን አስመልክቶ የተሰጠ ጋዜጣዊ መግለጫ፡፡
ከሁሉ አሰቀድመን እግዚአብሔር አምላካችን ለ2018 ዓ.ም ጾመ ፍልሰታ ለማርያም ሁላችንንም በሰላም በጤና ስላደረሰን እናመሰግነዋለን፡፡የተከበራችሁ አበው መነኮሳት፣ ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን፣ ካህናት እና ዲያቆናት፣ የሰንበት ት/ቤት ወጣቶች፣ ምዕመናን እና ወጣቶች በሀገር ውስጥ እና በውጭ ሀገር የምትኖሩ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ተከታዮች እንዲሁም ይህን መልእክት ለመላው ዓለም ለማስተላለፍ የተገኛችሁ የሚድያ አካላት በሙሉ በእግዚአብሔር ስም የከበረ ሰላምታችንን ጥንታዊ እና ታሪካዊ ከሆነው ከየካ ደብረ ሣህል ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን እናቀርባለን፡፡
“በኂሩተ ጻድቃን ትረትዕ ሀገር”
“በጻድቃን ልማት ከተማ ደስ ይላታል”
ምሳ 11፥10
እግዚአብሔር በንጉሱ ሰሎሞን ላይ አድሮ የተናገረውን መነሻ በማድረግ ልማት ለቤተከርስቲያን ፣ልማት ለሀገር፣ልማት ለማኅበረ ስብእ አስፈላጊ መሆኑን በማሰብ በአዲስ አበባ ሀገረ ስበከት በየካ ደብረ ሣህል ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን ለሚገነባው ቤተሰሊሆም ጠቅላላ ሆስፒታል የህንፃ ግንባታ የገቢ ማሰባሰቢያ የቀጥታ ስርጭት መርሃ ግብር የተዘጋጀ ጋዜጣዊ መግለጫ፡፡ የእግዚአበሔር ሰላም ከሁላችንም ጋር ይሁን፡፡ አሜን።
1. ታሪካዊ ዳራ እና የልማት መነሻ
ከአክሱም ዘመነ መንግሥት (በአባ ሰላማ ዘመን) የጀመረውና ከ1600 ዓመታት በላይ የዘለቀው የየካ ደብረ ሣህል ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን ታሪክ፤ የኢትዮጵያን ጥንታዊነትና የአዲስ አበባን ከተማ አመሰራረት የሚተርክ ህያው ቅርስ ነው።ይህ ታሪካዊ ደብር በአብርሃ ወአጽብሃ፣ በዳግማዊ አጼ ምኒልክና በንግሥት ጣይቱ፣ እንዲሁም በንግሥተ ነገሥታት ዘውዲቱ ዘመነ መንግሥት በርካታ የታሪክና የፈተና ምዕራፎችን አልፎ ዛሬ ላይ ደርሷል።
ደብሩ ከሃይማኖታዊ አገልግሎቱ ባሻገር፣ የአዲስ አበባ የመጀመሪያው የቀብር ቦታ በመሆን የሊቃውንቱና የካህናቱ እንዲሁም የታላቁ ሐኪም ወርቅነህ እሸቴን፣ የኢትዮጵያ ታላላቅ ጄነራሎችና ፊት አውራሪዎችን ዓጽም በክበር ማረፊያ ሆኗል፡፡ የጸሎትና ማህበራዊ አገልግሎት እንዲሁም ለአካባቢው አብያተ ክርስቲያናት መመስረት ባደረገው ከፍተኛ አስተዋጽኦ ይታወቃል። ዛሬ ይህ ታሪካዊ ደብር ጥንታዊ ታሪኩንና መንፈሳዊ ታላቅነቱን በዘመናዊ ማህበራዊ ልማት ለመድገም፣አካላዊ ፈውስን በሳይንሳዊ ሕክምና የመንፈሳዊ ፈውስን በፀሎትና በጠበል የሚያዋህድ ታላቅ የልማት ፕሮጀክት ይፋአድርጓል።
2. የሆስፒታሉ ይዘት፣ ራዕይና ሰብዓዊ ተልዕኮ
ቤተክርስቲያኑ ባለ 15 ወለል ማለትም (2 Basement+G+ 12ወለል) የሆነውን «ቤተሰሊሆም ጠቅላላ ሆስፒታል» ህንፃ ግንባታ የጀመረ ሲሆን፣ የመጀመሪያውን ምዕራፍ የመሰረት ቁፋሮና የአፈር ናዳ መከላከያ (ሾሪንግ) ሥራ በማጠናቀቅ ላይ ይገኛል።
ይህ በ1000 ካሬ ሜትር ቦታ ላይ የሚያርፈውና ባለ 250 የህሙማን ሕክምና መስጫ አልጋ አቅም የሚኖረው ዘመናዊ ሆስፒታል፤ የተመላላሽ ክሊኒኮችን፣ የፅኑ ሕክምና (ICU)፣ የቀዶ ጥገና ክፍሎችን እንዲሁም ለእናቶችና ሕጻናት ጤና፣ ለልብ ሕክምናና ለተላላፊ በሽታዎች መከላከያ የሚሆኑ ልዩ ልዩ ማዕከላትን ያካትታል። ተቋሙ የጤና አጠባበቅን እንደ ንግድ ሳይሆን እንደ ሰብዓዊና መንፈሳዊ አገልግሎት በመመልከት፣ለሁሉም የማህበረሰቡ አባላት በሙሉ ጥራት ያለው፣ ተደራሽና አቅምን ያገናዘበ የሕክምና አገልግሎት ያቀርባል።
3. የግንባታ ወጪ እና የገቢ ማሰባሰቢያ ጥሪ
በህንፃ ባለሙያዎች ጥናት መሠረት ለህንፃ ግንባታው አጠቃላይ ወጪ ብር 405,040,000 (አራት መቶ አምስትሚሊዮን አርባ ሺህ ብር) እንደሚሆን ተገምቷል።ይህ ወጪ በየጊዜው በሚታየው የዋጋ ንረት ምክንያት ሊጨምር እንደሚችል ይታሰባል፡፡
ይህንን ከፍተኛ ወጪ ለመሸፈንና ቀጣዩን ወሳኝ የግንባታምዕራፍ ለመጀመር ቤተ ክርስቲያኑ በአገር ውስጥና በውጭ አገር የሚኖሩ ምዕመናንን፣ የንግዱን ማህበረሰብና የልማት አጋሮችን ያሳተፈ የሀብት ማሰባሰቢያ ስልት ቀይሷል።
የደብሩ ሰበካ ጉባኤ እና የልማት ኮሚቴው ምዕመናን በሰጦታቸው ከእግዚአብሔር የሚያገኙትን በረከት በማሰብ፦ «ይህ ታላቅ የማህበራዊና የጤና ልማት ፕሮጀክት ፍጻሜ እንዲያገኝ የዓላማው ደጋፊዎች ሁሉ የእርዳታ እጃቸውን እንዲዘረጉና አሻራቸውን እንዲያኖሩ በሊቀ መላዕክት ቅዱስ ሚካኤል ስም እንማጸናለን» ሲል ጥሪውን ያስተላልፋል።
የገቢ ማሰባሰቢያ መርሃ-ግብር ዝርዝር፦
• ቀን፦ ነሐሴ 8፣ 9 እና 10 ቀን 2018 ዓ.ም
• ሰዓት፦ ከምሽቱ 12:00 ሰዓት ጀምሮ
የገቢ ማሰባሰቢያ የባንክ አማራጮች፦
• የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሂሳብቁጥር፦
1000000764087 እንዲሁም
አጭር ቁጥር 1277
• አባይ ባንክ ሂሳብ ቁጥር፦ 1227
• አዋሽ ባንክ ሂሳብ ቁጥር
013521784586601
• ስዊፍት ኮድ AWINETAA
• ወገን ፈንድ 👉 https://www.wegenfund.com/...
ለተጨማሪ መረጃ፦
• ስልክ ቁጥር፦
0945881188 እና 0945771188
• Email፦ Seyoumwgebrielgmail .com
ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን።
ከሁሉ አሰቀድመን እግዚአብሔር አምላካችን ለ2018 ዓ.ም ጾመ ፍልሰታ ለማርያም ሁላችንንም በሰላም በጤና ስላደረሰን እናመሰግነዋለን፡፡የተከበራችሁ አበው መነኮሳት፣ ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን፣ ካህናት እና ዲያቆናት፣ የሰንበት ት/ቤት ወጣቶች፣ ምዕመናን እና ወጣቶች በሀገር ውስጥ እና በውጭ ሀገር የምትኖሩ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ተከታዮች እንዲሁም ይህን መልእክት ለመላው ዓለም ለማስተላለፍ የተገኛችሁ የሚድያ አካላት በሙሉ በእግዚአብሔር ስም የከበረ ሰላምታችንን ጥንታዊ እና ታሪካዊ ከሆነው ከየካ ደብረ ሣህል ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን እናቀርባለን፡፡
“በኂሩተ ጻድቃን ትረትዕ ሀገር”
“በጻድቃን ልማት ከተማ ደስ ይላታል”
ምሳ 11፥10
እግዚአብሔር በንጉሱ ሰሎሞን ላይ አድሮ የተናገረውን መነሻ በማድረግ ልማት ለቤተከርስቲያን ፣ልማት ለሀገር፣ልማት ለማኅበረ ስብእ አስፈላጊ መሆኑን በማሰብ በአዲስ አበባ ሀገረ ስበከት በየካ ደብረ ሣህል ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን ለሚገነባው ቤተሰሊሆም ጠቅላላ ሆስፒታል የህንፃ ግንባታ የገቢ ማሰባሰቢያ የቀጥታ ስርጭት መርሃ ግብር የተዘጋጀ ጋዜጣዊ መግለጫ፡፡ የእግዚአበሔር ሰላም ከሁላችንም ጋር ይሁን፡፡ አሜን።
1. ታሪካዊ ዳራ እና የልማት መነሻ
ከአክሱም ዘመነ መንግሥት (በአባ ሰላማ ዘመን) የጀመረውና ከ1600 ዓመታት በላይ የዘለቀው የየካ ደብረ ሣህል ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን ታሪክ፤ የኢትዮጵያን ጥንታዊነትና የአዲስ አበባን ከተማ አመሰራረት የሚተርክ ህያው ቅርስ ነው።ይህ ታሪካዊ ደብር በአብርሃ ወአጽብሃ፣ በዳግማዊ አጼ ምኒልክና በንግሥት ጣይቱ፣ እንዲሁም በንግሥተ ነገሥታት ዘውዲቱ ዘመነ መንግሥት በርካታ የታሪክና የፈተና ምዕራፎችን አልፎ ዛሬ ላይ ደርሷል።
ደብሩ ከሃይማኖታዊ አገልግሎቱ ባሻገር፣ የአዲስ አበባ የመጀመሪያው የቀብር ቦታ በመሆን የሊቃውንቱና የካህናቱ እንዲሁም የታላቁ ሐኪም ወርቅነህ እሸቴን፣ የኢትዮጵያ ታላላቅ ጄነራሎችና ፊት አውራሪዎችን ዓጽም በክበር ማረፊያ ሆኗል፡፡ የጸሎትና ማህበራዊ አገልግሎት እንዲሁም ለአካባቢው አብያተ ክርስቲያናት መመስረት ባደረገው ከፍተኛ አስተዋጽኦ ይታወቃል። ዛሬ ይህ ታሪካዊ ደብር ጥንታዊ ታሪኩንና መንፈሳዊ ታላቅነቱን በዘመናዊ ማህበራዊ ልማት ለመድገም፣አካላዊ ፈውስን በሳይንሳዊ ሕክምና የመንፈሳዊ ፈውስን በፀሎትና በጠበል የሚያዋህድ ታላቅ የልማት ፕሮጀክት ይፋአድርጓል።
2. የሆስፒታሉ ይዘት፣ ራዕይና ሰብዓዊ ተልዕኮ
ቤተክርስቲያኑ ባለ 15 ወለል ማለትም (2 Basement+G+ 12ወለል) የሆነውን «ቤተሰሊሆም ጠቅላላ ሆስፒታል» ህንፃ ግንባታ የጀመረ ሲሆን፣ የመጀመሪያውን ምዕራፍ የመሰረት ቁፋሮና የአፈር ናዳ መከላከያ (ሾሪንግ) ሥራ በማጠናቀቅ ላይ ይገኛል።
ይህ በ1000 ካሬ ሜትር ቦታ ላይ የሚያርፈውና ባለ 250 የህሙማን ሕክምና መስጫ አልጋ አቅም የሚኖረው ዘመናዊ ሆስፒታል፤ የተመላላሽ ክሊኒኮችን፣ የፅኑ ሕክምና (ICU)፣ የቀዶ ጥገና ክፍሎችን እንዲሁም ለእናቶችና ሕጻናት ጤና፣ ለልብ ሕክምናና ለተላላፊ በሽታዎች መከላከያ የሚሆኑ ልዩ ልዩ ማዕከላትን ያካትታል። ተቋሙ የጤና አጠባበቅን እንደ ንግድ ሳይሆን እንደ ሰብዓዊና መንፈሳዊ አገልግሎት በመመልከት፣ለሁሉም የማህበረሰቡ አባላት በሙሉ ጥራት ያለው፣ ተደራሽና አቅምን ያገናዘበ የሕክምና አገልግሎት ያቀርባል።
3. የግንባታ ወጪ እና የገቢ ማሰባሰቢያ ጥሪ
በህንፃ ባለሙያዎች ጥናት መሠረት ለህንፃ ግንባታው አጠቃላይ ወጪ ብር 405,040,000 (አራት መቶ አምስትሚሊዮን አርባ ሺህ ብር) እንደሚሆን ተገምቷል።ይህ ወጪ በየጊዜው በሚታየው የዋጋ ንረት ምክንያት ሊጨምር እንደሚችል ይታሰባል፡፡
ይህንን ከፍተኛ ወጪ ለመሸፈንና ቀጣዩን ወሳኝ የግንባታምዕራፍ ለመጀመር ቤተ ክርስቲያኑ በአገር ውስጥና በውጭ አገር የሚኖሩ ምዕመናንን፣ የንግዱን ማህበረሰብና የልማት አጋሮችን ያሳተፈ የሀብት ማሰባሰቢያ ስልት ቀይሷል።
የደብሩ ሰበካ ጉባኤ እና የልማት ኮሚቴው ምዕመናን በሰጦታቸው ከእግዚአብሔር የሚያገኙትን በረከት በማሰብ፦ «ይህ ታላቅ የማህበራዊና የጤና ልማት ፕሮጀክት ፍጻሜ እንዲያገኝ የዓላማው ደጋፊዎች ሁሉ የእርዳታ እጃቸውን እንዲዘረጉና አሻራቸውን እንዲያኖሩ በሊቀ መላዕክት ቅዱስ ሚካኤል ስም እንማጸናለን» ሲል ጥሪውን ያስተላልፋል።
የገቢ ማሰባሰቢያ መርሃ-ግብር ዝርዝር፦
• ቀን፦ ነሐሴ 8፣ 9 እና 10 ቀን 2018 ዓ.ም
• ሰዓት፦ ከምሽቱ 12:00 ሰዓት ጀምሮ
የገቢ ማሰባሰቢያ የባንክ አማራጮች፦
• የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሂሳብቁጥር፦
1000000764087 እንዲሁም
አጭር ቁጥር 1277
• አባይ ባንክ ሂሳብ ቁጥር፦ 1227
• አዋሽ ባንክ ሂሳብ ቁጥር
013521784586601
• ስዊፍት ኮድ AWINETAA
• ወገን ፈንድ 👉 https://www.wegenfund.com/...
ለተጨማሪ መረጃ፦
• ስልክ ቁጥር፦
0945881188 እና 0945771188
• Email፦ Seyoumwgebrielgmail .com
ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን።
2 hours ago
ሴንቸሪ ፕሮሞሽን የ35ኛውን “ዘመን ገበያ የአዲስ ዓመት ኤክስፖ 2019” ሊያካሂድ ነው!
#fastmereja :-ሴንቸሪ ፕሮሞሽን እና ኤቨንትስ 35ተኛዉን ታላቅ የአዲስ አመት የንግድ ትርኢት እና ባዛር ከነሐሴ 15 እስከ ጳጉሜ 5 ቀን 2018 ዓ.ም. ለ21 ተከታታይ ቀናት በኤግዚቢሽን ማዕከል እና በመስቀል አደባባይ እንደሚያካሂድ በዛሬው ዕለት በሰጡት ይፋዊ ጋዜጣዊ መግለጫ አስታወቁ።
ባለፉት 27 ዓመታት ከ60 በላይ ታላላቅ ሁነቶችን እና 34 የንግድ ትርኢቶችን ያዘጋጀው ሴንቸሪ ፕሮሞሽን፤ የዘንድሮውን የ2019 ዓ.ም. የአዲስ ዓመት ኤክስፖ ለማዘጋጀት በኤግዚቢሽን ማዕከልና ገበያ ልማት ድርጅት የወጣውን ጨረታ በማሸነፍ ወደ ተለመደው ስራው መመለሱን አስታውቋል።
በዚህ የንግድ ትርኢት እና ባዛር ላይ ከ500 በላይ አምራቾች፣ አስመጪና ላኪዎች፣ የንግድ ወኪሎች እና ልዩ ልዩ አገልግሎት ሰጪ ድርጅቶች እንደሚሳተፉ ተገልጿል።
በዚህ የንግድ ትርኢት እና ባዛር ላይ የተለያዩ እጣዎች የተዘጋጁ ሲሆን በዚህም ላቅ ያሉ ሽልማቶች ተዘጋጅተዋል 1ኛ ዕጣ በኤሌክትሪክ ኃይል የሚሠራ ዘመናዊ አውቶሞቢል (መኪና) 2ኛ ዕጣ የቢ.ኤም.ደብሊው (BMW) ኤሌክትሪክሞተር ሳይክል እንዲሁም 3ኛ ዕጣ የኤሌክትሪክ ብስክሌት እንደሆነም ነዉ የተገለፀዉ።
በተጨማሪም ከነሐሴ 16 እስከ ጳጉሜ 5 ቀን ድረስ በየምሽቱ የተለያዩ የሙዚቃ ኮንሰርቶች የሚቀርቡ ሲሆን፤ ከነሐሴ 16 እስከ 21 ባሉት ቀናት ደግሞ ለአሸንዳ፣ አሸንድዬ እና ሶለል በዓላት የተዘጋጁ ልዩ የባህል ጭፈራዎችና የየዕለቱ የሽልማት ውድድሮች እንደሚካሄዱ ተገልጿል።
📷 ከበደ መክብብ
#fastmereja :-ሴንቸሪ ፕሮሞሽን እና ኤቨንትስ 35ተኛዉን ታላቅ የአዲስ አመት የንግድ ትርኢት እና ባዛር ከነሐሴ 15 እስከ ጳጉሜ 5 ቀን 2018 ዓ.ም. ለ21 ተከታታይ ቀናት በኤግዚቢሽን ማዕከል እና በመስቀል አደባባይ እንደሚያካሂድ በዛሬው ዕለት በሰጡት ይፋዊ ጋዜጣዊ መግለጫ አስታወቁ።
ባለፉት 27 ዓመታት ከ60 በላይ ታላላቅ ሁነቶችን እና 34 የንግድ ትርኢቶችን ያዘጋጀው ሴንቸሪ ፕሮሞሽን፤ የዘንድሮውን የ2019 ዓ.ም. የአዲስ ዓመት ኤክስፖ ለማዘጋጀት በኤግዚቢሽን ማዕከልና ገበያ ልማት ድርጅት የወጣውን ጨረታ በማሸነፍ ወደ ተለመደው ስራው መመለሱን አስታውቋል።
በዚህ የንግድ ትርኢት እና ባዛር ላይ ከ500 በላይ አምራቾች፣ አስመጪና ላኪዎች፣ የንግድ ወኪሎች እና ልዩ ልዩ አገልግሎት ሰጪ ድርጅቶች እንደሚሳተፉ ተገልጿል።
በዚህ የንግድ ትርኢት እና ባዛር ላይ የተለያዩ እጣዎች የተዘጋጁ ሲሆን በዚህም ላቅ ያሉ ሽልማቶች ተዘጋጅተዋል 1ኛ ዕጣ በኤሌክትሪክ ኃይል የሚሠራ ዘመናዊ አውቶሞቢል (መኪና) 2ኛ ዕጣ የቢ.ኤም.ደብሊው (BMW) ኤሌክትሪክሞተር ሳይክል እንዲሁም 3ኛ ዕጣ የኤሌክትሪክ ብስክሌት እንደሆነም ነዉ የተገለፀዉ።
በተጨማሪም ከነሐሴ 16 እስከ ጳጉሜ 5 ቀን ድረስ በየምሽቱ የተለያዩ የሙዚቃ ኮንሰርቶች የሚቀርቡ ሲሆን፤ ከነሐሴ 16 እስከ 21 ባሉት ቀናት ደግሞ ለአሸንዳ፣ አሸንድዬ እና ሶለል በዓላት የተዘጋጁ ልዩ የባህል ጭፈራዎችና የየዕለቱ የሽልማት ውድድሮች እንደሚካሄዱ ተገልጿል።
📷 ከበደ መክብብ
17 hours ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) "RSF አሁንም ኢትዮጵያ ውስጥ ወታደራዊ ካምፕ አለው" ሲሉ የኩምሩክ ግዛት አስተዳዳሪ ተናገሩ፡፡ የኩምሩክ ገዥ አብደል አቲ መሀመድ አልፋቂ የአካባቢው ነዋሪዎች ቀስ በቀስ መመለስ እንደጀመሩ አስታወቁ፡፡ ይህም በሰሜናዊ ኩምሩክ ውስጥ በሚገኙት ሁለት አስተዳደሮች ውስጥ መረጋጋት እየተፈጠረ መሆኑን እንደሚያሳይ ገልፀዋል፡፡
አልፋቂ ከሱዳን ሆራይዘን ጋር በተለይ ባደረጉት ቃለምልልስ አካባቢው በፈጥኖ ደራሽ ሀይሉ ወይንም RSF እጅ በነበረበት ወቅት የደረሰውን ጉዳት ለማወቅ አጠቃላይ ግምገማ እየተደረገ መሆኑን አስታውቀዋል፡፡ ጨምረውም ወሳኝ የሆኑ የህዝብ አገልግሎት መስጫዎች ከፍተኛ ጉዳት እንደደረሰባቸው ገልፀዋል፡፡ በከተማው ውስጥ የተበተኑ ያልፈነዱ ቦምቦች፣ አደገኛ እቃዎችና ሌሎች የጦርነት ቅሪቶች በብዛት መኖራቸውን ጠቅሰውም እነዚህን የማፅዳት ስራዎች በመከናወን ላይ እንደሚገኙም አስረድተዋል፡፡
በከተማው የተቀበሩ ፈንጂዎች ለማህበረሰቡ ትልቅ ስጋት መሆናቸውን ያስታወቁት ገዥው የተፈናቀሉ ነዋሪዎችን ሙሉ በሙሉ ለመመለስ የሚቻለው ይህ የማፅዳት ስራው በቴክኒክ ኮሚቴዎች ከተረጋገጠ በኋላ እንደሚሆን ገልፀዋል፡፡ የጤናና የውሀ መሰረተ ልማቶችን ጨምሮ ከፍተኛ ጉዳት መድረሱን የጠቀሱት ገዢው በማጠቃለያቸውም ‹‹ይህም ሆኖ RSF አሁንም ኢትዮጵያ ውስጥ ወታደራዊ ካምፕ አለው›› በማለት መናገራቸውን ጋዜጣው ዘግቧል፡፡
አልፋቂ ከሱዳን ሆራይዘን ጋር በተለይ ባደረጉት ቃለምልልስ አካባቢው በፈጥኖ ደራሽ ሀይሉ ወይንም RSF እጅ በነበረበት ወቅት የደረሰውን ጉዳት ለማወቅ አጠቃላይ ግምገማ እየተደረገ መሆኑን አስታውቀዋል፡፡ ጨምረውም ወሳኝ የሆኑ የህዝብ አገልግሎት መስጫዎች ከፍተኛ ጉዳት እንደደረሰባቸው ገልፀዋል፡፡ በከተማው ውስጥ የተበተኑ ያልፈነዱ ቦምቦች፣ አደገኛ እቃዎችና ሌሎች የጦርነት ቅሪቶች በብዛት መኖራቸውን ጠቅሰውም እነዚህን የማፅዳት ስራዎች በመከናወን ላይ እንደሚገኙም አስረድተዋል፡፡
በከተማው የተቀበሩ ፈንጂዎች ለማህበረሰቡ ትልቅ ስጋት መሆናቸውን ያስታወቁት ገዥው የተፈናቀሉ ነዋሪዎችን ሙሉ በሙሉ ለመመለስ የሚቻለው ይህ የማፅዳት ስራው በቴክኒክ ኮሚቴዎች ከተረጋገጠ በኋላ እንደሚሆን ገልፀዋል፡፡ የጤናና የውሀ መሰረተ ልማቶችን ጨምሮ ከፍተኛ ጉዳት መድረሱን የጠቀሱት ገዢው በማጠቃለያቸውም ‹‹ይህም ሆኖ RSF አሁንም ኢትዮጵያ ውስጥ ወታደራዊ ካምፕ አለው›› በማለት መናገራቸውን ጋዜጣው ዘግቧል፡፡
18 hours ago
በኮንታ ዞን ሙሉ በሙሉ ተፈጥሯዊነቱን የጠበቀ አዲስ የጫካ ቡና መገኘቱ ተበሰረ!
#fastmereja :-በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በሚገኘው ታሪካዊው ኮንታ ዞን፣ እስከ ዛሬ በሰው እጅ ያልተነካና ተፈጥሮአዊ ይዘቱን ሙሉ በሙሉ ጠብቆ የቆየ አዲስ የጫካ ቡና (Wild Forest Coffee) ተበሰረ።
ይህ በሰው እጅ ያልተተከለና «ያልተመነዘረ አረንጓዴ ወርቅ» የተባለው አዲስ የቡና ዘር የተገኘው፣ በኮንታ ዞን «ኦሽካ ዴንቻ» ጥቅጥቅ ጫካ ውስጥ በሚገኘው «አሜክ ኤጄቻ» በተሰኘ ልዩ ቦታ ላይ መሆኑ የተገለፀ ሲሆን አካባቢው ሰውና የዱር እንስሳት በተስማማ ሁኔታ የሚኖሩበት በመሆኑ፣ የቡናው ተፈጥሯዊ መዓዛና ጣዕም እጅግ ልዩ እንደሆነ ተገልጿል።
ድርጅቱ አዲሱ የቡና ዘር መገኘቱ ለሀገራችን አዲስ ዓለም አቀፍ ብራንድ ይዞ የሚመጣ መሆኑን ጠቁሞ፤ እንደ ጅማ፣ ይርጋጨፌ እና ሐረር ሁሉ «Konta Coffee» በሚል ስም ለሀገር ውስጥና ለዓለም አቀፍ ገበያ በመቅረብ፣ የኢትዮጵያን የውጭ ምንዛሪ ግኝት ወደ ላቀ ደረጃ ያሸጋግራል ብሏል።
በተጨማሪም ያልተነካውን የኮንታ የተፈጥሮ ጫካ እና የቡና መገኛ ቦታዎችን ለዓለም በማስተዋወቅ የኢኮ-ቱሪዝም ዘርፉን በከፍተኛ ሁኔታ እንደሚያነቃቃው ገልጿል።
የኮንታ ብሔረሰብ የሙዚቃ አቀንቃኝና የባህል አምባሳደር አርቲስት ወንድወሰን አበበ (ወንዴ ኮንታ) በበኩሉ፣ “«ኑ ቡና ጠጡ» የሚለው ጥሪ የቡና መጠጣት ሥነ-ሥርዓት ብቻ ሳይሆን የሰላም፣ የፍቅር፣ የጽኑ ጉርብትና እና የኢትዮጵያዊነት መስተጋብር ማሳያ ነው” ሲል ተናግሯል።
አርቲስቱ አክሎም ይህንን ውድ ተፈጥሮአዊ ሀብት ጠብቆ ላቆየው ማኅበረሰብ እውቅና መስጠትና ባህሉን ከኪነ-ጥበብ ጋር አዋህዶ ማቅረብ ታሪካዊ ኃላፊነት መሆኑን አብራርቷል።
ከዚሁ ጋር ተያይዞ፣ ለዕይታ ያልበቁና በምስል ያልተቀረፁ የባህል ትውፊቶችን ቅርፃቸውን እንደጠበቁ ለዓለም መድረክ ለማብቃት ሰፊ እንቅስቃሴ መጀመሩ ተገልጿል።
ይህንን ታሪካዊ ግኝት አስመልክቶ «ቶካ ፊልም መንደር እና ኢኮ ቱሪዝም» (Konta Coffee) በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ አዲሱን የጫካ ቡና ይፋ ለማድረግ "ኑ ቡና ጠጡ" የተሰኘ ታላቅ ሀገራዊ ጥሪና የመርሃ ግብር ዝግጅት ማድረጉን አስታውቋል።
በዚሁ መሠረት ቶካ ፊልም መንደር ከ«ኪን-ኢትዮጵያ የባህል ቡድን» እና ከ«ቤራ ኢንተርቴይንመንትና ኤቨንትስ» ጋር የጋራ የሥራ ስምምነት የተፈራረመ ሲሆን፣ በቅርቡም በጋራ ጋዜጣዊ መግለጫ እንደሚሰጡ አስታውቀዋል።
#fastmereja :-በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በሚገኘው ታሪካዊው ኮንታ ዞን፣ እስከ ዛሬ በሰው እጅ ያልተነካና ተፈጥሮአዊ ይዘቱን ሙሉ በሙሉ ጠብቆ የቆየ አዲስ የጫካ ቡና (Wild Forest Coffee) ተበሰረ።
ይህ በሰው እጅ ያልተተከለና «ያልተመነዘረ አረንጓዴ ወርቅ» የተባለው አዲስ የቡና ዘር የተገኘው፣ በኮንታ ዞን «ኦሽካ ዴንቻ» ጥቅጥቅ ጫካ ውስጥ በሚገኘው «አሜክ ኤጄቻ» በተሰኘ ልዩ ቦታ ላይ መሆኑ የተገለፀ ሲሆን አካባቢው ሰውና የዱር እንስሳት በተስማማ ሁኔታ የሚኖሩበት በመሆኑ፣ የቡናው ተፈጥሯዊ መዓዛና ጣዕም እጅግ ልዩ እንደሆነ ተገልጿል።
ድርጅቱ አዲሱ የቡና ዘር መገኘቱ ለሀገራችን አዲስ ዓለም አቀፍ ብራንድ ይዞ የሚመጣ መሆኑን ጠቁሞ፤ እንደ ጅማ፣ ይርጋጨፌ እና ሐረር ሁሉ «Konta Coffee» በሚል ስም ለሀገር ውስጥና ለዓለም አቀፍ ገበያ በመቅረብ፣ የኢትዮጵያን የውጭ ምንዛሪ ግኝት ወደ ላቀ ደረጃ ያሸጋግራል ብሏል።
በተጨማሪም ያልተነካውን የኮንታ የተፈጥሮ ጫካ እና የቡና መገኛ ቦታዎችን ለዓለም በማስተዋወቅ የኢኮ-ቱሪዝም ዘርፉን በከፍተኛ ሁኔታ እንደሚያነቃቃው ገልጿል።
የኮንታ ብሔረሰብ የሙዚቃ አቀንቃኝና የባህል አምባሳደር አርቲስት ወንድወሰን አበበ (ወንዴ ኮንታ) በበኩሉ፣ “«ኑ ቡና ጠጡ» የሚለው ጥሪ የቡና መጠጣት ሥነ-ሥርዓት ብቻ ሳይሆን የሰላም፣ የፍቅር፣ የጽኑ ጉርብትና እና የኢትዮጵያዊነት መስተጋብር ማሳያ ነው” ሲል ተናግሯል።
አርቲስቱ አክሎም ይህንን ውድ ተፈጥሮአዊ ሀብት ጠብቆ ላቆየው ማኅበረሰብ እውቅና መስጠትና ባህሉን ከኪነ-ጥበብ ጋር አዋህዶ ማቅረብ ታሪካዊ ኃላፊነት መሆኑን አብራርቷል።
ከዚሁ ጋር ተያይዞ፣ ለዕይታ ያልበቁና በምስል ያልተቀረፁ የባህል ትውፊቶችን ቅርፃቸውን እንደጠበቁ ለዓለም መድረክ ለማብቃት ሰፊ እንቅስቃሴ መጀመሩ ተገልጿል።
ይህንን ታሪካዊ ግኝት አስመልክቶ «ቶካ ፊልም መንደር እና ኢኮ ቱሪዝም» (Konta Coffee) በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ አዲሱን የጫካ ቡና ይፋ ለማድረግ "ኑ ቡና ጠጡ" የተሰኘ ታላቅ ሀገራዊ ጥሪና የመርሃ ግብር ዝግጅት ማድረጉን አስታውቋል።
በዚሁ መሠረት ቶካ ፊልም መንደር ከ«ኪን-ኢትዮጵያ የባህል ቡድን» እና ከ«ቤራ ኢንተርቴይንመንትና ኤቨንትስ» ጋር የጋራ የሥራ ስምምነት የተፈራረመ ሲሆን፣ በቅርቡም በጋራ ጋዜጣዊ መግለጫ እንደሚሰጡ አስታውቀዋል።
19 hours ago
"ኑ ቡና ጠጡ" ተብላቹኋል
* በኮንታ ዞን አዲስ የተፈጥሮ የጫካ ቡና መገኘቱን ይፋ ተደረገ
#ethiopia | በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ በሚገኘው በታሪካዊው ኮንታ ዞን እስከ ዛሬ በሰው እጅ ያልተነካና ተፈጥሮአዊነቱን ፍጹም ጠብቆ የቆየ አዲስ የተፈጥሮ ጫካ ቡና መገኘቱ ተበሰረ።
በኮንታ ዞን ጥቁርና ጥቅጥቅ ባለው «አሜክ ኤጄቻ» ጫካ ውስጥ የተገኘው የቡና ዘር የሀገራችንን የቡና ታሪክ አዲስ ምዕራፍ የሚያስጀምር መሆኑ ተገልጿል።
ይህንን ታሪካዊ ግኝት አስመልክቶ «ቶካ ፊልም መንደር እና ኢኮ ቱሪዝም» (Konta Coffee) በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ አዲሱን የጫካ ቡና ይፋ ለማድረግ "ኑ ቡና ጠጡ" የተሰኘ ታላቅ ሀገራዊ ጥሪና የመርሃ ግብር ዝግጅት ማድረጉን አስታውቋል።
ድርጅቱ አዲሱ የቡና ዘር መገኘቱ ለሀገራችን አዲስ ዓለም አቀፍ ብራንድ ይዞ የሚመጣ መሆኑን ገልጿል።
እንደ ጅማ ይርጋጨፌ እና ሐረር ሁሉ «Konta Coffee» በሚል ስም ለሀገር ውስጥና ለዓለም አቀፍ ገበያ በመቅረብ የኢትዮጵያን የውጭ ምንዛሪ ግኝት ወደ ላቀ ደረጃ ያሸጋግራል።
ያልተነካውን የኮንታ የተፈጥሮ ጫካ እና የቡና መገኛ ቦታዎችን ለዓለም በማስተዋወቅ የዘርፉን ቱሪዝም በከፍተኛ ሁኔታ ያነቃቃዋል ብሏል።
የኮንታ ብሔረሰብ የሙዚቃ አቀንቃኝና የባህል አምባሳደር አርቲስት ወንዴ ኮንታ እንዳለው "ኑ ቡና ጠጡ" የሚለው ጥሪ የቡና መጠጣት ሥነ-ሥርዓት ብቻ ሳይሆን የሰላም የፍቅር የጽኑ ጉርብትና እና የኢትዮጵያዊነት መስተጋብር ማሳያ ነው ።
ይህንን ውድ ተፈጥሮአዊ ሀብት ጠብቆ ላቆየው ማኅበረሰብ እውቅና መስጠትና ባህሉን ከኪነ ጥበብ ጋር አዋህዶ ማቅረብ ታሪካዊ ኃላፊነት ነው" ሲል ተናግሯል ።
ከዚሁ ጋር ተያይዞ ለዕይታ ያልበቁ የባህል ትውፊቶችን ለዓለም ለማስተዋወቅ ቶካ ፊልም መንደር እና ኢኮ ቱሪዝም ከኢትዮጵያ የባህል ቡድን እና ከቤራ ኢንተርቴይንመንት ጋር የጋራ የሥራ ስምምነት ተፈራርመዋል።
ሔኖክ ወ/ገብርኤል
#ethiopia #getutemesgen #getunews #discoverethiopia #kontacoffee #nubunatetu #ethiopiancoffee #wendekonta
* በኮንታ ዞን አዲስ የተፈጥሮ የጫካ ቡና መገኘቱን ይፋ ተደረገ
#ethiopia | በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ በሚገኘው በታሪካዊው ኮንታ ዞን እስከ ዛሬ በሰው እጅ ያልተነካና ተፈጥሮአዊነቱን ፍጹም ጠብቆ የቆየ አዲስ የተፈጥሮ ጫካ ቡና መገኘቱ ተበሰረ።
በኮንታ ዞን ጥቁርና ጥቅጥቅ ባለው «አሜክ ኤጄቻ» ጫካ ውስጥ የተገኘው የቡና ዘር የሀገራችንን የቡና ታሪክ አዲስ ምዕራፍ የሚያስጀምር መሆኑ ተገልጿል።
ይህንን ታሪካዊ ግኝት አስመልክቶ «ቶካ ፊልም መንደር እና ኢኮ ቱሪዝም» (Konta Coffee) በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ አዲሱን የጫካ ቡና ይፋ ለማድረግ "ኑ ቡና ጠጡ" የተሰኘ ታላቅ ሀገራዊ ጥሪና የመርሃ ግብር ዝግጅት ማድረጉን አስታውቋል።
ድርጅቱ አዲሱ የቡና ዘር መገኘቱ ለሀገራችን አዲስ ዓለም አቀፍ ብራንድ ይዞ የሚመጣ መሆኑን ገልጿል።
እንደ ጅማ ይርጋጨፌ እና ሐረር ሁሉ «Konta Coffee» በሚል ስም ለሀገር ውስጥና ለዓለም አቀፍ ገበያ በመቅረብ የኢትዮጵያን የውጭ ምንዛሪ ግኝት ወደ ላቀ ደረጃ ያሸጋግራል።
ያልተነካውን የኮንታ የተፈጥሮ ጫካ እና የቡና መገኛ ቦታዎችን ለዓለም በማስተዋወቅ የዘርፉን ቱሪዝም በከፍተኛ ሁኔታ ያነቃቃዋል ብሏል።
የኮንታ ብሔረሰብ የሙዚቃ አቀንቃኝና የባህል አምባሳደር አርቲስት ወንዴ ኮንታ እንዳለው "ኑ ቡና ጠጡ" የሚለው ጥሪ የቡና መጠጣት ሥነ-ሥርዓት ብቻ ሳይሆን የሰላም የፍቅር የጽኑ ጉርብትና እና የኢትዮጵያዊነት መስተጋብር ማሳያ ነው ።
ይህንን ውድ ተፈጥሮአዊ ሀብት ጠብቆ ላቆየው ማኅበረሰብ እውቅና መስጠትና ባህሉን ከኪነ ጥበብ ጋር አዋህዶ ማቅረብ ታሪካዊ ኃላፊነት ነው" ሲል ተናግሯል ።
ከዚሁ ጋር ተያይዞ ለዕይታ ያልበቁ የባህል ትውፊቶችን ለዓለም ለማስተዋወቅ ቶካ ፊልም መንደር እና ኢኮ ቱሪዝም ከኢትዮጵያ የባህል ቡድን እና ከቤራ ኢንተርቴይንመንት ጋር የጋራ የሥራ ስምምነት ተፈራርመዋል።
ሔኖክ ወ/ገብርኤል
#ethiopia #getutemesgen #getunews #discoverethiopia #kontacoffee #nubunatetu #ethiopiancoffee #wendekonta
Sponsored by
Surafel
23 hours ago
መንግሥት ሌብነትን እና ሕገወጥነትን ለመከላከል ጠንካራ እርምጃ እየወሰደ መሆኑን ገለጸ
በኢትዮጵያ ተግባራዊ እየተደረገ ያለውን ሰፊ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ለማደናቀፍ በሚንቀሳቀሱ እና የሀገር ሀብት በሚመዘብሩ አካላት ላይ መንግሥት የማያዳግም እርምጃ እየወሰደ መሆኑን አስታወቀ።
የኢፌዴሪ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ወይዘሮ እናትዓለም መለሰ ዛሬ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ፤ ኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት ፈጣን ልማትና ዕድገት እንድታረጋግጥ በርካታ ሥራዎች መሠራታቸውን ጠቅሰው፣ በዚህም ሰፋፊና አስደናቂ ሀገራዊ ውጤቶች መመዝገባቸውን ገልጸዋል፡፡ በዚህ ሂደት ግን ይህ ውጤት ጉዞው አልጋ በአልጋ እንዳልነበር አመላክተዋል ። ከተለያዩ ሀገራዊና ዓለም አቀፋዊ ተግዳሮቶች ባሻገር፣ ሕገ-ወጥነት እና የሙስና ተግባራት የልማቱ ዋነኛ ፈተና ሆነው መቆየታቸውንም ክብርት ሚኒስትሯ አብራርተዋል።
እንደ ሚኒስትሯ ገለጻ፣ የሕገ-ወጥነት ችግር በአንድ ወገን ብቻ የሚፈጸም ሳይሆን በርካታ የኅብረተሰብ ክፍሎችን የሚያጠቃልል መሆኑን ገልጸው ከውስጥም ከውጪም ያሉ በርካታ ኃይሎች በተደራጀ መንገድ ሲንቀሳቀሱ ነበር፡፡ በንግዱ ማኅበረሰብ፣ በልማት ድርጅቶች፣ በመንግሥት መዋቅር፣ በግለሰቦች እና በተገልጋዮች ጭምር በተደራጀ መንገድ በስፋት የሚታይ ነው።
እነዚህ አካላት ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያውን ከቁጥጥር ውጭ ለማድረግ በፋይናንስ እና በንግድ ሥርዐቱ ውስጥ ሰርገው በመግባት ከፍተኛ የኢኮኖሚ አሻጥር ሲፈጽሙ ቆይተዋል" ያሉት ወይዘሮ እናትዓለም፤ ድርጊቱ ሀገሪቱ የውጭ ምንዛሬ እንድታጣ፣ የዋጋ ንረትና ኮንትሮባንድ እንዲባባስ እንዲሁም በፍጆታ እቃዎች ላይ ሰው ሠራሽ እጥረት እንዲፈጠር ማድረጉን አስታውቀዋል። ይህንን የተደራጀ አሻጥር ለመግታት መንግሥት እና የሚመለከታቸው የሕግ አካላት ባከናወኑት ሰፊ ኦፕሬሽን አሻጥሩን ማክሸፍ መቻሉ ተገልጿል።
በሌላ በኩል በመንግሥት አገልግሎት ሰጪ እና አስተዳደር አካላት እንዲሁም የሕዝብ ተቋማት ውስጥ የተሰገሰጉ ሌቦችን በማጽዳት ረገድ መንግሥት ቁርጠኛ እርምጃ እየወሰደ እንደሚገኝ ያስታወቁት ወ/ሮ እናትዓለም በሕዝብ ሀብት ላይ ከፍተኛ ምዝበራ የፈጸሙ እና ተቋማዊ አሻጥር በሠሩ አመራሮች እና ሌሎች የጥቅም ትስስሮችና ድርጅቶች ላይ የማያዳግም እርምጃ መወሰዱንም አስታውቀዋል። በተለይም በሚከተሉት ቁልፍ ዘርፎች ላይ በተፈጸሙ ወንጀሎች ሰፊ ማጣራት ተደርጎ ተጠያቂነት ሰፍኗል ሲሉ ገልጸዋል፡
በመንግሥት አገልግሎት ሰጪ እና አስተዳደር አካላት፣ እንዲሁም ልዩ ልዩ የልማት ዘርፎች ውስጥ የተፈጸሙ ዋና ዋና የሙስና እና አሻጥር ወንጀሎችን ለማረም በተወሰዱት ሰፊ ኦፕሬሽኖች እና ሕግ የማስከበር እርምጃዎች ተጨባጭ ውጤቶች ተመዝግበዋል። ከማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ጋር በተያያዘ ማሻሻያውን ለማደናቀፍ በማሰብ መሠረታዊ የፍጆታ ምርቶችን በማከማቸት እጥረት እንዲፈጠርና ዋጋ እንዲንር ሲያደርጉ የነበሩ 13 አቅራቢ ድርጅቶች ባለቤቶች ላይ ማስጠንቀቂያ ተሰጥቷል፤ ሕገ-ወጥ ተግባር ሲፈጽሙ በነበሩ ከ7 ሺህ በላይ የንግድ ድርጅቶችና መጋዘኖች ላይ የማሸግ እርምጃ ተወስዷል።
በፋይናንስ ተቋማት እና የገንዘብ ዝውውር፡ በሕገ-ወጥ የገንዘብ ዝውውር፣ በሐዋላ እና በጥቁር ገበያ ተሳታፊ የሆኑ 169 ኢትዮጵያውያንና የውጭ ሀገር ዜጎች በሕግ ተጠያቂ እንዲሆኑ ተደርጓል። በተደራጀ መንገድ ከንግድ ባንክ ደንበኞች አካውንት ላይ በማጭበርበር ገንዘብ የወሰዱ 36 ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ውለው የባንክ ሒሳባቸው እንዲታገድ ተደርጓል።
ለሕገ-ወጥ ዝውውር ሽፋን ይሰጡ የነበሩ 7 የክሪፕቶ ካረንሲ መተግበሪያዎች በሀገር ውስጥ እንዳይሠሩ ሙሉ በሙሉ ታግደዋል፤ ምርት ልከው የውጭ ምንዛሬ ተመላሽ ያላደረጉ 29 ላኪ የንግድ ድርጅቶችና ግለሰቦች ላይም የህግ ተጠያቂነት ሰፍኗል።
በቤቲንግ እና ፊንቴክ ቢዝነሶች፡ የደንበኞችን መረጃ በመደበቅ መንግሥትን ግብር ያጭበረበሩ፣ ገቢያቸውን የሰወሩ እና ሕገ-ወጥ የገንዘብ ዝውውር በፈጸሙ 38 የቤቲንግ ድርጅቶች ላይ እርምጃ ተወስዶ ባለቤቶቻቸው በቁጥጥር ስር ውለዋል፤ የእነዚህ ሕገ-ወጥ ተቋማት የባንክ ሒሳብ ታግዷል፤
በማዕድን ዘርፍ ሕገ-ወጥ ዝውውር፡ የወርቅ ምርትን ከገበያ ውጭ በኮንትሮባንድ በማስወጣት ወንጀል የተሳተፉ የመንግሥት ኃላፊዎችን፣ የፀጥታ መዋቅር አመራሮችን፣ አምራቾችን እና የውጭ ዜጎችን ጨምሮ 183 ግለሰቦች በሕግ ተጠያቂ ተደርገዋል። በወንጀሉ የተሳተፉ የውጭ ሀገር ዜጎች ከሀገር እንዲወጡ ተደርገዋል፤ ሕገ-ወጥ ወርቅ፣ የወርቅ ሚዛንና ማቅለጫ፣ የተለያዩ የውጭ ሀገራት ገንዘቦች፣ እንዲሁም የጦር መሳሪያዎች በቁጥጥር ስር ውለዋል።
ከነዳጅ አቅርቦት እና ሎጂስቲክስ አንጻር፡ በሕገ-ወጥ መንገድ የሽፋን ደብዳቤዎችን በማዘጋጀት፣ ነዳጅ በመደበቅ እና አየር በአየር በመሸጥ ወንጀል የተሳተፉ 38 የመንግሥት አመራሮች በሕግ ተጠያቂ እንዲሆኑ ተደርጓል። በተጨማሪም በሀገር አቀፍ ደረጃ በሕገ-ወጥ የነዳጅ ንግድ ላይ የተሰማሩ ከ650 በላይ ግለሰቦች፣ ማደያዎች እና አቅራቢ ኩባንያዎች ላይ የህግ እርምጃ ተወስዷል።
በአፈር ማዳበሪያ ግዢ አሻጥር፡ በተቋሙ የጥቅም ትስስር በመፍጠር ጥራት የጎደለውና ጊዜው ያለፈበት የአፈር ማዳበሪያ ግዢ እንዲፈጸም በማድረግ ሆን ብለው ችግር በፈጠሩ የግብርና ሚኒስቴር አመራሮች ላይ የወንጀል ተጠያቂነት እርምጃ ተወስዷል።
በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል (EEP)፡ ተገቢው መመሪያ በሌለበት ሁኔታ ከ36 የዳታ ማይኒንግ ድርጅቶች ጋር ሕገ-ወጥ የኃይል ሽያጭ ውል የፈጸሙ 4 ከፍተኛ አመራሮች ላይ እርምጃ ተወስዷል። የኤሌክትሪክ ኃይል ስርቆት የፈጸሙ ድርጅቶች እና ግለሰቦችም እንዲሁ በሕግ እንዲጠየቁ ተደርጓል።
በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር እና የሰዎች ዝውውር የውጭ ሀገር የሥራ ስምሪት ሲስተምን በማዛባት እና ጉቦ በመቀበል ወንጀል የተሳተፉ 8 ከፍተኛ አመራሮችና ሠራተኞች በሕግ ቁጥጥር ስር ውለዋል። እንዲሁም በሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውር ላይ የተሰማሩ 44 ደላሎች እና አዘዋዋሪዎች በሕግ ቁጥጥር ስር ሲውሉ፣ ሕገ-ወጥ ፈቃድ የነበራቸው ተቋማት ሙሉ በሙሉ ታሽገዋል።
በገቢዎችና ጉምሩክ ዘርፍ፡ የግብር ውሳኔዎችን በመቀነስ፣ ሐሰተኛ ደረሰኞች በማወራረድ፣ እና በሲስተም መረጃ በማጥፋት የመንግሥት ገቢን ባሳጡ አካላት ላይ ኦፕሬሽን ተካሂዷል። በራሳቸው፣ በዘመድ እና በሹፌሮቻቸው አካውንት በመጠቀም የጥቅም ትስስር የፈጠሩ 109 ተጠርጣሪዎች ተለይተው ከእነዚህ መካከል 91 ግለሰቦች በሕግ ቁጥጥር ስር ውለዋል።
መንግሥት የልማት እንቅፋት የሆኑትን ሙስና እና ሌብነት እንደማንኛውም ፈተና በጽናት እየተጋፈጣቸው መሆኑን ሚኒስትሯ አረጋግጠዋል።
መንግሥት ሌብነትን ለማጥፋት ዘመናዊ አሠራሮችን በመዘርጋት እና በዲሲፕሊን የታነጸ አመራር ለመገንባት ቁርጠኛ ነው" ያሉት ወይዘሮ እናትዓለም፤ ሕዝቡ በስፋት የሚያነሣቸውን "ሌብነትን አስቁሙልን" ጥያቄዎች ለመመለስ የተጀመረዉ ጠንካራ እርምጃ ውጤታማ እንዲሆኑ ማኅበረሰቡ ሙስናን በማጋለጥ፣ ሕጋዊ መብቱን በመደለያ ባለመጠየቅ እና ከሕገወጦች ጋር ባለመተባበር ከመንግሥት ጎን በመቆም ሀገርን ከሕገወጥነትና ሙስና የመከላከል ታሪካዊ ኃላፊነቱን እንዲወጣ ጥሪ አቅርበዋል።
የኢፌዴሪ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት
በኢትዮጵያ ተግባራዊ እየተደረገ ያለውን ሰፊ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ለማደናቀፍ በሚንቀሳቀሱ እና የሀገር ሀብት በሚመዘብሩ አካላት ላይ መንግሥት የማያዳግም እርምጃ እየወሰደ መሆኑን አስታወቀ።
የኢፌዴሪ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ወይዘሮ እናትዓለም መለሰ ዛሬ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ፤ ኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት ፈጣን ልማትና ዕድገት እንድታረጋግጥ በርካታ ሥራዎች መሠራታቸውን ጠቅሰው፣ በዚህም ሰፋፊና አስደናቂ ሀገራዊ ውጤቶች መመዝገባቸውን ገልጸዋል፡፡ በዚህ ሂደት ግን ይህ ውጤት ጉዞው አልጋ በአልጋ እንዳልነበር አመላክተዋል ። ከተለያዩ ሀገራዊና ዓለም አቀፋዊ ተግዳሮቶች ባሻገር፣ ሕገ-ወጥነት እና የሙስና ተግባራት የልማቱ ዋነኛ ፈተና ሆነው መቆየታቸውንም ክብርት ሚኒስትሯ አብራርተዋል።
እንደ ሚኒስትሯ ገለጻ፣ የሕገ-ወጥነት ችግር በአንድ ወገን ብቻ የሚፈጸም ሳይሆን በርካታ የኅብረተሰብ ክፍሎችን የሚያጠቃልል መሆኑን ገልጸው ከውስጥም ከውጪም ያሉ በርካታ ኃይሎች በተደራጀ መንገድ ሲንቀሳቀሱ ነበር፡፡ በንግዱ ማኅበረሰብ፣ በልማት ድርጅቶች፣ በመንግሥት መዋቅር፣ በግለሰቦች እና በተገልጋዮች ጭምር በተደራጀ መንገድ በስፋት የሚታይ ነው።
እነዚህ አካላት ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያውን ከቁጥጥር ውጭ ለማድረግ በፋይናንስ እና በንግድ ሥርዐቱ ውስጥ ሰርገው በመግባት ከፍተኛ የኢኮኖሚ አሻጥር ሲፈጽሙ ቆይተዋል" ያሉት ወይዘሮ እናትዓለም፤ ድርጊቱ ሀገሪቱ የውጭ ምንዛሬ እንድታጣ፣ የዋጋ ንረትና ኮንትሮባንድ እንዲባባስ እንዲሁም በፍጆታ እቃዎች ላይ ሰው ሠራሽ እጥረት እንዲፈጠር ማድረጉን አስታውቀዋል። ይህንን የተደራጀ አሻጥር ለመግታት መንግሥት እና የሚመለከታቸው የሕግ አካላት ባከናወኑት ሰፊ ኦፕሬሽን አሻጥሩን ማክሸፍ መቻሉ ተገልጿል።
በሌላ በኩል በመንግሥት አገልግሎት ሰጪ እና አስተዳደር አካላት እንዲሁም የሕዝብ ተቋማት ውስጥ የተሰገሰጉ ሌቦችን በማጽዳት ረገድ መንግሥት ቁርጠኛ እርምጃ እየወሰደ እንደሚገኝ ያስታወቁት ወ/ሮ እናትዓለም በሕዝብ ሀብት ላይ ከፍተኛ ምዝበራ የፈጸሙ እና ተቋማዊ አሻጥር በሠሩ አመራሮች እና ሌሎች የጥቅም ትስስሮችና ድርጅቶች ላይ የማያዳግም እርምጃ መወሰዱንም አስታውቀዋል። በተለይም በሚከተሉት ቁልፍ ዘርፎች ላይ በተፈጸሙ ወንጀሎች ሰፊ ማጣራት ተደርጎ ተጠያቂነት ሰፍኗል ሲሉ ገልጸዋል፡
በመንግሥት አገልግሎት ሰጪ እና አስተዳደር አካላት፣ እንዲሁም ልዩ ልዩ የልማት ዘርፎች ውስጥ የተፈጸሙ ዋና ዋና የሙስና እና አሻጥር ወንጀሎችን ለማረም በተወሰዱት ሰፊ ኦፕሬሽኖች እና ሕግ የማስከበር እርምጃዎች ተጨባጭ ውጤቶች ተመዝግበዋል። ከማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ጋር በተያያዘ ማሻሻያውን ለማደናቀፍ በማሰብ መሠረታዊ የፍጆታ ምርቶችን በማከማቸት እጥረት እንዲፈጠርና ዋጋ እንዲንር ሲያደርጉ የነበሩ 13 አቅራቢ ድርጅቶች ባለቤቶች ላይ ማስጠንቀቂያ ተሰጥቷል፤ ሕገ-ወጥ ተግባር ሲፈጽሙ በነበሩ ከ7 ሺህ በላይ የንግድ ድርጅቶችና መጋዘኖች ላይ የማሸግ እርምጃ ተወስዷል።
በፋይናንስ ተቋማት እና የገንዘብ ዝውውር፡ በሕገ-ወጥ የገንዘብ ዝውውር፣ በሐዋላ እና በጥቁር ገበያ ተሳታፊ የሆኑ 169 ኢትዮጵያውያንና የውጭ ሀገር ዜጎች በሕግ ተጠያቂ እንዲሆኑ ተደርጓል። በተደራጀ መንገድ ከንግድ ባንክ ደንበኞች አካውንት ላይ በማጭበርበር ገንዘብ የወሰዱ 36 ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ውለው የባንክ ሒሳባቸው እንዲታገድ ተደርጓል።
ለሕገ-ወጥ ዝውውር ሽፋን ይሰጡ የነበሩ 7 የክሪፕቶ ካረንሲ መተግበሪያዎች በሀገር ውስጥ እንዳይሠሩ ሙሉ በሙሉ ታግደዋል፤ ምርት ልከው የውጭ ምንዛሬ ተመላሽ ያላደረጉ 29 ላኪ የንግድ ድርጅቶችና ግለሰቦች ላይም የህግ ተጠያቂነት ሰፍኗል።
በቤቲንግ እና ፊንቴክ ቢዝነሶች፡ የደንበኞችን መረጃ በመደበቅ መንግሥትን ግብር ያጭበረበሩ፣ ገቢያቸውን የሰወሩ እና ሕገ-ወጥ የገንዘብ ዝውውር በፈጸሙ 38 የቤቲንግ ድርጅቶች ላይ እርምጃ ተወስዶ ባለቤቶቻቸው በቁጥጥር ስር ውለዋል፤ የእነዚህ ሕገ-ወጥ ተቋማት የባንክ ሒሳብ ታግዷል፤
በማዕድን ዘርፍ ሕገ-ወጥ ዝውውር፡ የወርቅ ምርትን ከገበያ ውጭ በኮንትሮባንድ በማስወጣት ወንጀል የተሳተፉ የመንግሥት ኃላፊዎችን፣ የፀጥታ መዋቅር አመራሮችን፣ አምራቾችን እና የውጭ ዜጎችን ጨምሮ 183 ግለሰቦች በሕግ ተጠያቂ ተደርገዋል። በወንጀሉ የተሳተፉ የውጭ ሀገር ዜጎች ከሀገር እንዲወጡ ተደርገዋል፤ ሕገ-ወጥ ወርቅ፣ የወርቅ ሚዛንና ማቅለጫ፣ የተለያዩ የውጭ ሀገራት ገንዘቦች፣ እንዲሁም የጦር መሳሪያዎች በቁጥጥር ስር ውለዋል።
ከነዳጅ አቅርቦት እና ሎጂስቲክስ አንጻር፡ በሕገ-ወጥ መንገድ የሽፋን ደብዳቤዎችን በማዘጋጀት፣ ነዳጅ በመደበቅ እና አየር በአየር በመሸጥ ወንጀል የተሳተፉ 38 የመንግሥት አመራሮች በሕግ ተጠያቂ እንዲሆኑ ተደርጓል። በተጨማሪም በሀገር አቀፍ ደረጃ በሕገ-ወጥ የነዳጅ ንግድ ላይ የተሰማሩ ከ650 በላይ ግለሰቦች፣ ማደያዎች እና አቅራቢ ኩባንያዎች ላይ የህግ እርምጃ ተወስዷል።
በአፈር ማዳበሪያ ግዢ አሻጥር፡ በተቋሙ የጥቅም ትስስር በመፍጠር ጥራት የጎደለውና ጊዜው ያለፈበት የአፈር ማዳበሪያ ግዢ እንዲፈጸም በማድረግ ሆን ብለው ችግር በፈጠሩ የግብርና ሚኒስቴር አመራሮች ላይ የወንጀል ተጠያቂነት እርምጃ ተወስዷል።
በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል (EEP)፡ ተገቢው መመሪያ በሌለበት ሁኔታ ከ36 የዳታ ማይኒንግ ድርጅቶች ጋር ሕገ-ወጥ የኃይል ሽያጭ ውል የፈጸሙ 4 ከፍተኛ አመራሮች ላይ እርምጃ ተወስዷል። የኤሌክትሪክ ኃይል ስርቆት የፈጸሙ ድርጅቶች እና ግለሰቦችም እንዲሁ በሕግ እንዲጠየቁ ተደርጓል።
በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር እና የሰዎች ዝውውር የውጭ ሀገር የሥራ ስምሪት ሲስተምን በማዛባት እና ጉቦ በመቀበል ወንጀል የተሳተፉ 8 ከፍተኛ አመራሮችና ሠራተኞች በሕግ ቁጥጥር ስር ውለዋል። እንዲሁም በሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውር ላይ የተሰማሩ 44 ደላሎች እና አዘዋዋሪዎች በሕግ ቁጥጥር ስር ሲውሉ፣ ሕገ-ወጥ ፈቃድ የነበራቸው ተቋማት ሙሉ በሙሉ ታሽገዋል።
በገቢዎችና ጉምሩክ ዘርፍ፡ የግብር ውሳኔዎችን በመቀነስ፣ ሐሰተኛ ደረሰኞች በማወራረድ፣ እና በሲስተም መረጃ በማጥፋት የመንግሥት ገቢን ባሳጡ አካላት ላይ ኦፕሬሽን ተካሂዷል። በራሳቸው፣ በዘመድ እና በሹፌሮቻቸው አካውንት በመጠቀም የጥቅም ትስስር የፈጠሩ 109 ተጠርጣሪዎች ተለይተው ከእነዚህ መካከል 91 ግለሰቦች በሕግ ቁጥጥር ስር ውለዋል።
መንግሥት የልማት እንቅፋት የሆኑትን ሙስና እና ሌብነት እንደማንኛውም ፈተና በጽናት እየተጋፈጣቸው መሆኑን ሚኒስትሯ አረጋግጠዋል።
መንግሥት ሌብነትን ለማጥፋት ዘመናዊ አሠራሮችን በመዘርጋት እና በዲሲፕሊን የታነጸ አመራር ለመገንባት ቁርጠኛ ነው" ያሉት ወይዘሮ እናትዓለም፤ ሕዝቡ በስፋት የሚያነሣቸውን "ሌብነትን አስቁሙልን" ጥያቄዎች ለመመለስ የተጀመረዉ ጠንካራ እርምጃ ውጤታማ እንዲሆኑ ማኅበረሰቡ ሙስናን በማጋለጥ፣ ሕጋዊ መብቱን በመደለያ ባለመጠየቅ እና ከሕገወጦች ጋር ባለመተባበር ከመንግሥት ጎን በመቆም ሀገርን ከሕገወጥነትና ሙስና የመከላከል ታሪካዊ ኃላፊነቱን እንዲወጣ ጥሪ አቅርበዋል።
የኢፌዴሪ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት
24 hours ago
በሙስናና ሕገ-ወጥ አሠራር የተሳተፉ አካላት ላይ የሕግ እርምጃ ተወሰደ
በኢትዮጵያ ተግባራዊ እየተደረገ ያለውን ሰፊ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ለማደናቀፍ በሚንቀሳቀሱ እና የሀገር ሀብት በሚመዘብሩ አካላት ላይ መንግሥት የማያዳግም እርምጃ እየወሰደ መሆኑን አስታወቀ።
የኢፌዴሪ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ወይዘሮ እናትዓለም መለሰ ዛሬ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ፤ ኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት ፈጣን ልማትና ዕድገት እንድታረጋግጥ በርካታ ሥራዎች መሠራታቸውን ጠቅሰው፣ በዚህም ሰፋፊና አስደናቂ ሀገራዊ ውጤቶች መመዝገባቸውን ገልጸዋል። በዚህ ሂደት ግን ይህ ውጤት ጉዞው አልጋ በአልጋ እንዳልነበር አመላክተዋል። ከተለያዩ ሀገራዊና ዓለም አቀፋዊ ተግዳሮቶች ባሻገር፣ ሕገ-ወጥነት እና የሙስና ተግባራት የልማቱ ዋነኛ ፈተና ሆነው መቆየታቸውንም ክብርት ሚኒስትሯ አብራርተዋል።
እንደ ሚኒስትሯ ገለጻ፣ የሕገ-ወጥነት ችግር በአንድ ወገን ብቻ የሚፈጸም ሳይሆን በርካታ የኅብረተሰብ ክፍሎችን የሚያጠቃልል መሆኑን ገልጸው ከውስጥም ከውጪም ያሉ በርካታ ኃይሎች በተደራጀ መንገድ ሲንቀሳቀሱ ነበር። በንግዱ ማኅበረሰብ፣ በልማት ድርጅቶች፣ በመንግሥት መዋቅር፣ በግለሰቦች እና በተገልጋዮች ጭምር በተደራጀ መንገድ በስፋት የሚታይ ነው።
እነዚህ አካላት ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያውን ከቁጥጥር ውጭ ለማድረግ በፋይናንስ እና በንግድ ሥርዐቱ ውስጥ ሰርገው በመግባት ከፍተኛ የኢኮኖሚ አሻጥር ሲፈጽሙ ቆይተዋል" ያሉት ወይዘሮ እናትዓለም፤ ድርጊቱ ሀገሪቱ የውጭ ምንዛሬ እንድታጣ፣ የዋጋ ንረትና ኮንትሮባንድ እንዲባባስ እንዲሁም በፍጆታ እቃዎች ላይ ሰው ሠራሽ እጥረት እንዲፈጠር ማድረጉን አስታውቀዋል። ይህንን የተደራጀ አሻጥር ለመግታት መንግሥት እና የሚመለከታቸው የሕግ አካላት ባከናወኑት ሰፊ ኦፕሬሽን አሻጥሩን ማክሸፍ መቻሉ ተገልጿል።
በሌላ በኩል በመንግሥት አገልግሎት ሰጪ እና አስተዳደር አካላት እንዲሁም የሕዝብ ተቋማት ውስጥ የተሰገሰጉ ሌቦችን በማጽዳት ረገድ መንግሥት ቁርጠኛ እርምጃ እየወሰደ እንደሚገኝ ያስታወቁት ወ/ሮ እናትዓለም በሕዝብ ሀብት ላይ ከፍተኛ ምዝበራ የፈጸሙ እና ተቋማዊ አሻጥር በሠሩ አመራሮች እና ሌሎች የጥቅም ትስስሮችና ድርጅቶች ላይ የማያዳግም እርምጃ መወሰዱንም አስታውቀዋል። በተለይም በሚከተሉት ቁልፍ ዘርፎች ላይ በተፈጸሙ ወንጀሎች ሰፊ ማጣራት ተደርጎ ተጠያቂነት ሰፍኗል ሲሉ ገልጸዋል።
በመንግሥት አገልግሎት ሰጪ እና አስተዳደር አካላት፣ እንዲሁም ልዩ ልዩ የልማት ዘርፎች ውስጥ የተፈጸሙ ዋና ዋና የሙስና እና አሻጥር ወንጀሎችን ለማረም በተወሰዱት ሰፊ ኦፕሬሽኖች እና ሕግ የማስከበር እርምጃዎች ተጨባጭ ውጤቶች ተመዝግበዋል። ከማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ጋር በተያያዘ ማሻሻያውን ለማደናቀፍ በማሰብ መሠረታዊ የፍጆታ ምርቶችን በማከማቸት እጥረት እንዲፈጠርና ዋጋ እንዲንር ሲያደርጉ የነበሩ 13 አቅራቢ ድርጅቶች ባለቤቶች ላይ ማስጠንቀቂያ ተሰጥቷል፤ ሕገ-ወጥ ተግባር ሲፈጽሙ በነበሩ ከ7 ሺህ በላይ የንግድ ድርጅቶችና መጋዘኖች ላይ የማሸግ እርምጃ ተወስዷል።
በፋይናንስ ተቋማት እና የገንዘብ ዝውውር፡ በሕገ-ወጥ የገንዘብ ዝውውር፣ በሐዋላ እና በጥቁር ገበያ ተሳታፊ የሆኑ 169 ኢትዮጵያውያንና የውጭ ሀገር ዜጎች በሕግ ተጠያቂ እንዲሆኑ ተደርጓል። በተደራጀ መንገድ ከንግድ ባንክ ደንበኞች አካውንት ላይ በማጭበርበር ገንዘብ የወሰዱ 36 ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ውለው የባንክ ሒሳባቸው እንዲታገድ ተደርጓል።
ለሕገ-ወጥ ዝውውር ሽፋን ይሰጡ የነበሩ 7 የክሪፕቶ ካረንሲ መተግበሪያዎች በሀገር ውስጥ እንዳይሠሩ ሙሉ በሙሉ ታግደዋል፤ ምርት ልከው የውጭ ምንዛሬ ተመላሽ ያላደረጉ 29 ላኪ የንግድ ድርጅቶችና ግለሰቦች ላይም የህግ ተጠያቂነት ሰፍኗል።
በቤቲንግ እና ፊንቴክ ቢዝነሶች፡ የደንበኞችን መረጃ በመደበቅ መንግሥትን ግብር ያጭበረበሩ፣ ገቢያቸውን የሰወሩ እና ሕገ-ወጥ የገንዘብ ዝውውር በፈጸሙ 38 የቤቲንግ ድርጅቶች ላይ እርምጃ ተወስዶ ባለቤቶቻቸው በቁጥጥር ስር ውለዋል፤ የእነዚህ ሕገ-ወጥ ተቋማት የባንክ ሒሳብ ታግዷል፤
በማዕድን ዘርፍ ሕገ-ወጥ ዝውውር፡ የወርቅ ምርትን ከገበያ ውጭ በኮንትሮባንድ በማስወጣት ወንጀል የተሳተፉ የመንግሥት ኃላፊዎችን፣ የፀጥታ መዋቅር አመራሮችን፣ አምራቾችን እና የውጭ ዜጎችን ጨምሮ 183 ግለሰቦች በሕግ ተጠያቂ ተደርገዋል። በወንጀሉ የተሳተፉ የውጭ ሀገር ዜጎች ከሀገር እንዲወጡ ተደርገዋል፤ ሕገ-ወጥ ወርቅ፣ የወርቅ ሚዛንና ማቅለጫ፣ የተለያዩ የውጭ ሀገራት ገንዘቦች፣ እንዲሁም የጦር መሳሪያዎች በቁጥጥር ስር ውለዋል።
ከነዳጅ አቅርቦት እና ሎጂስቲክስ አንጻር፡ በሕገ-ወጥ መንገድ የሽፋን ደብዳቤዎችን በማዘጋጀት፣ ነዳጅ በመደበቅ እና አየር በአየር በመሸጥ ወንጀል የተሳተፉ 38 የመንግሥት አመራሮች በሕግ ተጠያቂ እንዲሆኑ ተደርጓል። በተጨማሪም በሀገር አቀፍ ደረጃ በሕገ-ወጥ የነዳጅ ንግድ ላይ የተሰማሩ ከ650 በላይ ግለሰቦች፣ ማደያዎች እና አቅራቢ ኩባንያዎች ላይ የህግ እርምጃ ተወስዷል።
በአፈር ማዳበሪያ ግዢ አሻጥር፡ በተቋሙ የጥቅም ትስስር በመፍጠር ጥራት የጎደለውና ጊዜው ያለፈበት የአፈር ማዳበሪያ ግዢ እንዲፈጸም በማድረግ ሆን ብለው ችግር በፈጠሩ የግብርና ሚኒስቴር አመራሮች ላይ የወንጀል ተጠያቂነት እርምጃ ተወስዷል።
በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል (EEP)፡ ተገቢው መመሪያ በሌለበት ሁኔታ ከ36 የዳታ ማይኒንግ ድርጅቶች ጋር ሕገ-ወጥ የኃይል ሽያጭ ውል የፈጸሙ 4 ከፍተኛ አመራሮች ላይ እርምጃ ተወስዷል። የኤሌክትሪክ ኃይል ስርቆት የፈጸሙ ድርጅቶች እና ግለሰቦችም እንዲሁ በሕግ እንዲጠየቁ ተደርጓል።
በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር እና የሰዎች ዝውውር የውጭ ሀገር የሥራ ስምሪት ሲስተምን በማዛባት እና ጉቦ በመቀበል ወንጀል የተሳተፉ 8 ከፍተኛ አመራሮችና ሠራተኞች በሕግ ቁጥጥር ስር ውለዋል። እንዲሁም በሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውር ላይ የተሰማሩ 44 ደላሎች እና አዘዋዋሪዎች በሕግ ቁጥጥር ስር ሲውሉ፣ ሕገ-ወጥ ፈቃድ የነበራቸው ተቋማት ሙሉ በሙሉ ታሽገዋል።
በገቢዎችና ጉምሩክ ዘርፍ፡ የግብር ውሳኔዎችን በመቀነስ፣ ሐሰተኛ ደረሰኞች በማወራረድ፣ እና በሲስተም መረጃ በማጥፋት የመንግሥት ገቢን ባሳጡ አካላት ላይ ኦፕሬሽን ተካሂዷል።
በራሳቸው፣ በዘመድ እና በሹፌሮቻቸው አካውንት በመጠቀም የጥቅም ትስስር የፈጠሩ 109 ተጠርጣሪዎች ተለይተው ከእነዚህ መካከል 91 ግለሰቦች በሕግ ቁጥጥር ስር ውለዋል።
መንግሥት የልማት እንቅፋት የሆኑትን ሙስና እና ሌብነት እንደማንኛውም ፈተና በጽናት እየተጋፈጣቸው መሆኑን ሚኒስትሯ አረጋግጠዋል።
መንግሥት ሌብነትን ለማጥፋት ዘመናዊ አሠራሮችን በመዘርጋት እና በዲሲፕሊን የታነጸ አመራር ለመገንባት ቁርጠኛ ነው" ያሉት ወይዘሮ እናትዓለም፤ ሕዝቡ በስፋት የሚያነሣቸውን "ሌብነትን አስቁሙልን" ጥያቄዎች ለመመለስ የተጀመረዉ ጠንካራ እርምጃ ውጤታማ እንዲሆኑ ማኅበረሰቡ ሙስናን በማጋለጥ፣ ሕጋዊ መብቱን በመደለያ ባለመጠየቅ እና ከሕገወጦች ጋር ባለመተባበር ከመንግሥት ጎን በመቆም ሀገርን ከሕገወጥነትና ሙስና የመከላከል ታሪካዊ ኃላፊነቱን እንዲወጣ ጥሪ አቅርበዋል።
Via EBC
በኢትዮጵያ ተግባራዊ እየተደረገ ያለውን ሰፊ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ለማደናቀፍ በሚንቀሳቀሱ እና የሀገር ሀብት በሚመዘብሩ አካላት ላይ መንግሥት የማያዳግም እርምጃ እየወሰደ መሆኑን አስታወቀ።
የኢፌዴሪ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ወይዘሮ እናትዓለም መለሰ ዛሬ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ፤ ኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት ፈጣን ልማትና ዕድገት እንድታረጋግጥ በርካታ ሥራዎች መሠራታቸውን ጠቅሰው፣ በዚህም ሰፋፊና አስደናቂ ሀገራዊ ውጤቶች መመዝገባቸውን ገልጸዋል። በዚህ ሂደት ግን ይህ ውጤት ጉዞው አልጋ በአልጋ እንዳልነበር አመላክተዋል። ከተለያዩ ሀገራዊና ዓለም አቀፋዊ ተግዳሮቶች ባሻገር፣ ሕገ-ወጥነት እና የሙስና ተግባራት የልማቱ ዋነኛ ፈተና ሆነው መቆየታቸውንም ክብርት ሚኒስትሯ አብራርተዋል።
እንደ ሚኒስትሯ ገለጻ፣ የሕገ-ወጥነት ችግር በአንድ ወገን ብቻ የሚፈጸም ሳይሆን በርካታ የኅብረተሰብ ክፍሎችን የሚያጠቃልል መሆኑን ገልጸው ከውስጥም ከውጪም ያሉ በርካታ ኃይሎች በተደራጀ መንገድ ሲንቀሳቀሱ ነበር። በንግዱ ማኅበረሰብ፣ በልማት ድርጅቶች፣ በመንግሥት መዋቅር፣ በግለሰቦች እና በተገልጋዮች ጭምር በተደራጀ መንገድ በስፋት የሚታይ ነው።
እነዚህ አካላት ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያውን ከቁጥጥር ውጭ ለማድረግ በፋይናንስ እና በንግድ ሥርዐቱ ውስጥ ሰርገው በመግባት ከፍተኛ የኢኮኖሚ አሻጥር ሲፈጽሙ ቆይተዋል" ያሉት ወይዘሮ እናትዓለም፤ ድርጊቱ ሀገሪቱ የውጭ ምንዛሬ እንድታጣ፣ የዋጋ ንረትና ኮንትሮባንድ እንዲባባስ እንዲሁም በፍጆታ እቃዎች ላይ ሰው ሠራሽ እጥረት እንዲፈጠር ማድረጉን አስታውቀዋል። ይህንን የተደራጀ አሻጥር ለመግታት መንግሥት እና የሚመለከታቸው የሕግ አካላት ባከናወኑት ሰፊ ኦፕሬሽን አሻጥሩን ማክሸፍ መቻሉ ተገልጿል።
በሌላ በኩል በመንግሥት አገልግሎት ሰጪ እና አስተዳደር አካላት እንዲሁም የሕዝብ ተቋማት ውስጥ የተሰገሰጉ ሌቦችን በማጽዳት ረገድ መንግሥት ቁርጠኛ እርምጃ እየወሰደ እንደሚገኝ ያስታወቁት ወ/ሮ እናትዓለም በሕዝብ ሀብት ላይ ከፍተኛ ምዝበራ የፈጸሙ እና ተቋማዊ አሻጥር በሠሩ አመራሮች እና ሌሎች የጥቅም ትስስሮችና ድርጅቶች ላይ የማያዳግም እርምጃ መወሰዱንም አስታውቀዋል። በተለይም በሚከተሉት ቁልፍ ዘርፎች ላይ በተፈጸሙ ወንጀሎች ሰፊ ማጣራት ተደርጎ ተጠያቂነት ሰፍኗል ሲሉ ገልጸዋል።
በመንግሥት አገልግሎት ሰጪ እና አስተዳደር አካላት፣ እንዲሁም ልዩ ልዩ የልማት ዘርፎች ውስጥ የተፈጸሙ ዋና ዋና የሙስና እና አሻጥር ወንጀሎችን ለማረም በተወሰዱት ሰፊ ኦፕሬሽኖች እና ሕግ የማስከበር እርምጃዎች ተጨባጭ ውጤቶች ተመዝግበዋል። ከማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ጋር በተያያዘ ማሻሻያውን ለማደናቀፍ በማሰብ መሠረታዊ የፍጆታ ምርቶችን በማከማቸት እጥረት እንዲፈጠርና ዋጋ እንዲንር ሲያደርጉ የነበሩ 13 አቅራቢ ድርጅቶች ባለቤቶች ላይ ማስጠንቀቂያ ተሰጥቷል፤ ሕገ-ወጥ ተግባር ሲፈጽሙ በነበሩ ከ7 ሺህ በላይ የንግድ ድርጅቶችና መጋዘኖች ላይ የማሸግ እርምጃ ተወስዷል።
በፋይናንስ ተቋማት እና የገንዘብ ዝውውር፡ በሕገ-ወጥ የገንዘብ ዝውውር፣ በሐዋላ እና በጥቁር ገበያ ተሳታፊ የሆኑ 169 ኢትዮጵያውያንና የውጭ ሀገር ዜጎች በሕግ ተጠያቂ እንዲሆኑ ተደርጓል። በተደራጀ መንገድ ከንግድ ባንክ ደንበኞች አካውንት ላይ በማጭበርበር ገንዘብ የወሰዱ 36 ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ውለው የባንክ ሒሳባቸው እንዲታገድ ተደርጓል።
ለሕገ-ወጥ ዝውውር ሽፋን ይሰጡ የነበሩ 7 የክሪፕቶ ካረንሲ መተግበሪያዎች በሀገር ውስጥ እንዳይሠሩ ሙሉ በሙሉ ታግደዋል፤ ምርት ልከው የውጭ ምንዛሬ ተመላሽ ያላደረጉ 29 ላኪ የንግድ ድርጅቶችና ግለሰቦች ላይም የህግ ተጠያቂነት ሰፍኗል።
በቤቲንግ እና ፊንቴክ ቢዝነሶች፡ የደንበኞችን መረጃ በመደበቅ መንግሥትን ግብር ያጭበረበሩ፣ ገቢያቸውን የሰወሩ እና ሕገ-ወጥ የገንዘብ ዝውውር በፈጸሙ 38 የቤቲንግ ድርጅቶች ላይ እርምጃ ተወስዶ ባለቤቶቻቸው በቁጥጥር ስር ውለዋል፤ የእነዚህ ሕገ-ወጥ ተቋማት የባንክ ሒሳብ ታግዷል፤
በማዕድን ዘርፍ ሕገ-ወጥ ዝውውር፡ የወርቅ ምርትን ከገበያ ውጭ በኮንትሮባንድ በማስወጣት ወንጀል የተሳተፉ የመንግሥት ኃላፊዎችን፣ የፀጥታ መዋቅር አመራሮችን፣ አምራቾችን እና የውጭ ዜጎችን ጨምሮ 183 ግለሰቦች በሕግ ተጠያቂ ተደርገዋል። በወንጀሉ የተሳተፉ የውጭ ሀገር ዜጎች ከሀገር እንዲወጡ ተደርገዋል፤ ሕገ-ወጥ ወርቅ፣ የወርቅ ሚዛንና ማቅለጫ፣ የተለያዩ የውጭ ሀገራት ገንዘቦች፣ እንዲሁም የጦር መሳሪያዎች በቁጥጥር ስር ውለዋል።
ከነዳጅ አቅርቦት እና ሎጂስቲክስ አንጻር፡ በሕገ-ወጥ መንገድ የሽፋን ደብዳቤዎችን በማዘጋጀት፣ ነዳጅ በመደበቅ እና አየር በአየር በመሸጥ ወንጀል የተሳተፉ 38 የመንግሥት አመራሮች በሕግ ተጠያቂ እንዲሆኑ ተደርጓል። በተጨማሪም በሀገር አቀፍ ደረጃ በሕገ-ወጥ የነዳጅ ንግድ ላይ የተሰማሩ ከ650 በላይ ግለሰቦች፣ ማደያዎች እና አቅራቢ ኩባንያዎች ላይ የህግ እርምጃ ተወስዷል።
በአፈር ማዳበሪያ ግዢ አሻጥር፡ በተቋሙ የጥቅም ትስስር በመፍጠር ጥራት የጎደለውና ጊዜው ያለፈበት የአፈር ማዳበሪያ ግዢ እንዲፈጸም በማድረግ ሆን ብለው ችግር በፈጠሩ የግብርና ሚኒስቴር አመራሮች ላይ የወንጀል ተጠያቂነት እርምጃ ተወስዷል።
በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል (EEP)፡ ተገቢው መመሪያ በሌለበት ሁኔታ ከ36 የዳታ ማይኒንግ ድርጅቶች ጋር ሕገ-ወጥ የኃይል ሽያጭ ውል የፈጸሙ 4 ከፍተኛ አመራሮች ላይ እርምጃ ተወስዷል። የኤሌክትሪክ ኃይል ስርቆት የፈጸሙ ድርጅቶች እና ግለሰቦችም እንዲሁ በሕግ እንዲጠየቁ ተደርጓል።
በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር እና የሰዎች ዝውውር የውጭ ሀገር የሥራ ስምሪት ሲስተምን በማዛባት እና ጉቦ በመቀበል ወንጀል የተሳተፉ 8 ከፍተኛ አመራሮችና ሠራተኞች በሕግ ቁጥጥር ስር ውለዋል። እንዲሁም በሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውር ላይ የተሰማሩ 44 ደላሎች እና አዘዋዋሪዎች በሕግ ቁጥጥር ስር ሲውሉ፣ ሕገ-ወጥ ፈቃድ የነበራቸው ተቋማት ሙሉ በሙሉ ታሽገዋል።
በገቢዎችና ጉምሩክ ዘርፍ፡ የግብር ውሳኔዎችን በመቀነስ፣ ሐሰተኛ ደረሰኞች በማወራረድ፣ እና በሲስተም መረጃ በማጥፋት የመንግሥት ገቢን ባሳጡ አካላት ላይ ኦፕሬሽን ተካሂዷል።
በራሳቸው፣ በዘመድ እና በሹፌሮቻቸው አካውንት በመጠቀም የጥቅም ትስስር የፈጠሩ 109 ተጠርጣሪዎች ተለይተው ከእነዚህ መካከል 91 ግለሰቦች በሕግ ቁጥጥር ስር ውለዋል።
መንግሥት የልማት እንቅፋት የሆኑትን ሙስና እና ሌብነት እንደማንኛውም ፈተና በጽናት እየተጋፈጣቸው መሆኑን ሚኒስትሯ አረጋግጠዋል።
መንግሥት ሌብነትን ለማጥፋት ዘመናዊ አሠራሮችን በመዘርጋት እና በዲሲፕሊን የታነጸ አመራር ለመገንባት ቁርጠኛ ነው" ያሉት ወይዘሮ እናትዓለም፤ ሕዝቡ በስፋት የሚያነሣቸውን "ሌብነትን አስቁሙልን" ጥያቄዎች ለመመለስ የተጀመረዉ ጠንካራ እርምጃ ውጤታማ እንዲሆኑ ማኅበረሰቡ ሙስናን በማጋለጥ፣ ሕጋዊ መብቱን በመደለያ ባለመጠየቅ እና ከሕገወጦች ጋር ባለመተባበር ከመንግሥት ጎን በመቆም ሀገርን ከሕገወጥነትና ሙስና የመከላከል ታሪካዊ ኃላፊነቱን እንዲወጣ ጥሪ አቅርበዋል።
Via EBC
1 day ago
የከተማ አስተዳደሩ በአነስተኛ የንግድ ስራ ላይ የደረጃ ‹‹ለ›› ግብር ከፋዮች እንዲበረታቱ ፣ የግብር ጫና እንዳይደርስባቸውና ትርፋማነታቸውን በማጎልበት ወደ ቀጣይ ደረጃ እንዲሸጋገሩ በቁርጠኛነት እየሰራ መሆኑን ቢሮው አስታወቀ ፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ በደረጃ ግብር ከፋዮች አከፋፈል ፣በሚነሱ ጥያቄዎችና ቅሬታዎች አፈታት ዙሪያ ለሚዲያ ተቋማት ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቷል ።
ቢሮው ባለፉት 2 አመታት ሰፋፊ የሪፎርም ተግባራት ማከናወኑን በጋዜጣዊ መግለጫው የተገለፀ ሲሆን የሪፎርም ተግባራቱ መሰረታዊ ዓላማዎችም ፍትሐዊ የግብር አሰባሰብ ስርዐት መዘርጋት ፣ የመልካም አስተዳደር እና የአገልግሎት አሰጣጥ እንዲሁም የሌብነትና ብልሹ አሰራሮችን መቅረፍ መሆናቸው ተጠቁሟል፡፡
የ2018 የግብር ዘመን የደረጃ ‹‹ለ›› ግብር ከፋዮች ጋር በተያያዘም አብዛኞቹ ግብር ከፋዮች በተቋሙ በተዘረጋ የኦንላይን የክፍያ ስርዓት መወጣታቸውና የተቀሩትም እየከፈሉ ናቸው ተብሏል፡፡
በተጨማሪም በከተማዋ በተለያዩ ንግዶች ፣ በኪራይና በራይድ የንግድ ዘርፎች የተሰማሩ 456 ሺህ 433 የደረጃ ግብር ከፋዮች የሚገኙ መሆናቸው የተጠቆመ ሲሆን ከእነዚህ ግብር ከፋዮች በአጠቃላይ 9.2 ቢሊዮን ብር ለመሰብሰብ መታቀዱ ተመላክቷል፡፡
ይህ ዓመታዊ የደረጃ ‹‹ለ›. ግብር ከፋዮች ገቢ በመንግስትና በግል ድርጅት ውስጥ ከሚገኙ ተቀጣሪ ደሞዝተኞች ዓመታዊ ደሞዝ ገቢ ግብር ጋር ሲነፃፀር በጣም አነስተኛ እንደሆነ ተገልጿል
ይህም በዋነኛነት ዐላማው የከተማ አስተዳደሩ በአነስተኛ የንግድ ስራ ላይ የተሰማሩ ነጋዴዎች እንዲበረታቱ፣ የግብር ጫና እንዳይደርስባቸውና ትርፋማነታቸውን በማጎልበት ወደ ቀጣይ ደረጃ እንዲሸጋገሩ ካለው አቋምና ቁርጠኛነት የመነጨ መሆኑም ተብራርቷል፡፡
በመሆኑም እስከ ሀምሌ 25 ድረስ ዓመታዊ ግብራችሁን እንድትከፍሉ መልዕክት በስልካችሁ የተላከላችሁ ግብር ከፋዮች በሙሉ እስከ ሀምሌ 30/2018 ዓ.ም ድረስ የግብር ግዴታችሁን በኦንላይን በመክፈል ከቅጣትና ወለድ እራሳችሁን እንዲጠብቁ ጥሪ ተላልፏል፡፡
ይሁንና በተለያዩ ምክንያቶች ቴክስት ያልደረሳችሁ ግብር ከፋዮች እንዲሁም ከሀምሌ 25 በኃላ ቴክሰት( መልዕክት ) የተላከላችሁ ግብር ከፋዮች ወደ ቅጣት የማይገቡ በመሆኑ እስከ ነሀሴ 20/2018 ዓ.ም ዓመታዊ ግብራችውን መክፈል እንደሚችሉ በመግለፅ ቴክስት ያልተላከላቸው ግብር ከፋዮች ባሉበት ሆነው በትዕግስት እንዲጠባበቁ ቢሮው ይገልፃል ፡፡
በተያያዘም ቴክስት (መልዕክት ) ከተላከለት በኃላ ‹‹ግብር በዛብኝ›› የሚል ቅሬታ ላለው ማንኛውም ግብር ከፋይ የቅሬታ አፈታት ስርዓት ተዘርግቶ ወደ ተግባር የተገባ መሆኑን የተገለፀ ሲሆን ቅሬታ ያለው ግብር ከፋይ በወረዳ ደረጃ ቅሬታ አቅርቦ መረጃው ለክፍለ ከተማ ከተላከ በኃላ በክፍለ ከተማ በተደራጀ የቀን ገቢ ገማች አማካኝነት ድጋሚ የቀን ገቢ ግምት በማካሄድ ቅሬታዎች የሚፈቱበት አሰራር መዘርጋቱ ተገልፆል፡፡
ከቅድመ ታክስ ክፍያ ጋር በተያያዘ ለደረጃ ‹‹ለ›› ግብር ከፋዮች በቴክስት የተላከ ዓመታዊ የግብር መጠንም ግብር ከፋዮች በቅድመ ታክስ የከፈሉትን የገንዘብ መጠን ተቀናሽ በማድረግ የተላከ እንደሆነም በጋዜጣዊ መግለጫው ተመላክቷል፡፡ በ2019 በጀት አመት እንደ ከተማ 502.27 ቢሊየን ፣ በገቢዎች ቢሮ 380 ቢሊየን ብር ገቢን በፍትሐዊነት ለመሠብሰብ መታቀዱም ተገልፆል፡፡
አዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ በደረጃ ግብር ከፋዮች አከፋፈል ፣በሚነሱ ጥያቄዎችና ቅሬታዎች አፈታት ዙሪያ ለሚዲያ ተቋማት ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቷል ።
ቢሮው ባለፉት 2 አመታት ሰፋፊ የሪፎርም ተግባራት ማከናወኑን በጋዜጣዊ መግለጫው የተገለፀ ሲሆን የሪፎርም ተግባራቱ መሰረታዊ ዓላማዎችም ፍትሐዊ የግብር አሰባሰብ ስርዐት መዘርጋት ፣ የመልካም አስተዳደር እና የአገልግሎት አሰጣጥ እንዲሁም የሌብነትና ብልሹ አሰራሮችን መቅረፍ መሆናቸው ተጠቁሟል፡፡
የ2018 የግብር ዘመን የደረጃ ‹‹ለ›› ግብር ከፋዮች ጋር በተያያዘም አብዛኞቹ ግብር ከፋዮች በተቋሙ በተዘረጋ የኦንላይን የክፍያ ስርዓት መወጣታቸውና የተቀሩትም እየከፈሉ ናቸው ተብሏል፡፡
በተጨማሪም በከተማዋ በተለያዩ ንግዶች ፣ በኪራይና በራይድ የንግድ ዘርፎች የተሰማሩ 456 ሺህ 433 የደረጃ ግብር ከፋዮች የሚገኙ መሆናቸው የተጠቆመ ሲሆን ከእነዚህ ግብር ከፋዮች በአጠቃላይ 9.2 ቢሊዮን ብር ለመሰብሰብ መታቀዱ ተመላክቷል፡፡
ይህ ዓመታዊ የደረጃ ‹‹ለ›. ግብር ከፋዮች ገቢ በመንግስትና በግል ድርጅት ውስጥ ከሚገኙ ተቀጣሪ ደሞዝተኞች ዓመታዊ ደሞዝ ገቢ ግብር ጋር ሲነፃፀር በጣም አነስተኛ እንደሆነ ተገልጿል
ይህም በዋነኛነት ዐላማው የከተማ አስተዳደሩ በአነስተኛ የንግድ ስራ ላይ የተሰማሩ ነጋዴዎች እንዲበረታቱ፣ የግብር ጫና እንዳይደርስባቸውና ትርፋማነታቸውን በማጎልበት ወደ ቀጣይ ደረጃ እንዲሸጋገሩ ካለው አቋምና ቁርጠኛነት የመነጨ መሆኑም ተብራርቷል፡፡
በመሆኑም እስከ ሀምሌ 25 ድረስ ዓመታዊ ግብራችሁን እንድትከፍሉ መልዕክት በስልካችሁ የተላከላችሁ ግብር ከፋዮች በሙሉ እስከ ሀምሌ 30/2018 ዓ.ም ድረስ የግብር ግዴታችሁን በኦንላይን በመክፈል ከቅጣትና ወለድ እራሳችሁን እንዲጠብቁ ጥሪ ተላልፏል፡፡
ይሁንና በተለያዩ ምክንያቶች ቴክስት ያልደረሳችሁ ግብር ከፋዮች እንዲሁም ከሀምሌ 25 በኃላ ቴክሰት( መልዕክት ) የተላከላችሁ ግብር ከፋዮች ወደ ቅጣት የማይገቡ በመሆኑ እስከ ነሀሴ 20/2018 ዓ.ም ዓመታዊ ግብራችውን መክፈል እንደሚችሉ በመግለፅ ቴክስት ያልተላከላቸው ግብር ከፋዮች ባሉበት ሆነው በትዕግስት እንዲጠባበቁ ቢሮው ይገልፃል ፡፡
በተያያዘም ቴክስት (መልዕክት ) ከተላከለት በኃላ ‹‹ግብር በዛብኝ›› የሚል ቅሬታ ላለው ማንኛውም ግብር ከፋይ የቅሬታ አፈታት ስርዓት ተዘርግቶ ወደ ተግባር የተገባ መሆኑን የተገለፀ ሲሆን ቅሬታ ያለው ግብር ከፋይ በወረዳ ደረጃ ቅሬታ አቅርቦ መረጃው ለክፍለ ከተማ ከተላከ በኃላ በክፍለ ከተማ በተደራጀ የቀን ገቢ ገማች አማካኝነት ድጋሚ የቀን ገቢ ግምት በማካሄድ ቅሬታዎች የሚፈቱበት አሰራር መዘርጋቱ ተገልፆል፡፡
ከቅድመ ታክስ ክፍያ ጋር በተያያዘ ለደረጃ ‹‹ለ›› ግብር ከፋዮች በቴክስት የተላከ ዓመታዊ የግብር መጠንም ግብር ከፋዮች በቅድመ ታክስ የከፈሉትን የገንዘብ መጠን ተቀናሽ በማድረግ የተላከ እንደሆነም በጋዜጣዊ መግለጫው ተመላክቷል፡፡ በ2019 በጀት አመት እንደ ከተማ 502.27 ቢሊየን ፣ በገቢዎች ቢሮ 380 ቢሊየን ብር ገቢን በፍትሐዊነት ለመሠብሰብ መታቀዱም ተገልፆል፡፡
አዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ
1 day ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የዋይት ሀውስ ፕሬስ ሴክሬታሪ ካሮላይን ሌቪት፣ የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በካምፕ ዴቪድ በተካሄደ ስብሰባ ላይ በሚሳኤል ክምችት እጥረት ዙሪያ ከመከላከያ ሚኒስትሩ ፒት ሄግሴዝ ጋር ተጋጭተዋል ሲል 'ዋሽንግተን ፖስት' ያወጣውን ዘገባ ውድቅ አደረጉ።
ጋዜጣው በዘገባው ትራምፕ በረጅም ርቀት ተምዘግዛጊ ሚሳኤሎች እና በአየር መከላከያ መሳሪያዎች እጥረት ዙሪያ ለምን የተሳሳተ መረጃ እንደተሰጣቸው ጠንከር ያለ ማብራሪያ መጠየቃቸውን አስነብቦ ነበር። በተጨማሪም፣ ይህ የተሟጠጠ የመሳሪያ ክምችት ትራምፕ በኢራን ላይ ተጨማሪ ሰፋፊ ጥቃቶችን ላለመክፈት ባሳለፉት ውሳኔ ላይ ተጽዕኖ ማሳደሩን ዘግቧል።
በትራምፕ እና በሄግሴዝ መካከል በነበረው ስብሰባ ላይ በአካል መታደማቸውን የገለጹት ሌቪት፣ የጋዜጣውን ዘገባ "የሀሰት ዜና" ሲሉ አጣጥለውታል።
"ይህ ነገር በጭራሽ አልተፈጠረም፤ ለዋሽንግተን ፖስትም ይህንኑ ደጋግመን ነግረናቸዋል" ያሉት ፕሬስ ሴክሬታሪዋ፣ በመቀጠልም ትራምፕ "ሚኒስትሩን እንደሚወዷቸው እና እጅግ አስደናቂ ስራ እየሰሩ እንደሆነ እንደሚያስቡ" አክለው ገልጸዋል።
ጋዜጣው በዘገባው ትራምፕ በረጅም ርቀት ተምዘግዛጊ ሚሳኤሎች እና በአየር መከላከያ መሳሪያዎች እጥረት ዙሪያ ለምን የተሳሳተ መረጃ እንደተሰጣቸው ጠንከር ያለ ማብራሪያ መጠየቃቸውን አስነብቦ ነበር። በተጨማሪም፣ ይህ የተሟጠጠ የመሳሪያ ክምችት ትራምፕ በኢራን ላይ ተጨማሪ ሰፋፊ ጥቃቶችን ላለመክፈት ባሳለፉት ውሳኔ ላይ ተጽዕኖ ማሳደሩን ዘግቧል።
በትራምፕ እና በሄግሴዝ መካከል በነበረው ስብሰባ ላይ በአካል መታደማቸውን የገለጹት ሌቪት፣ የጋዜጣውን ዘገባ "የሀሰት ዜና" ሲሉ አጣጥለውታል።
"ይህ ነገር በጭራሽ አልተፈጠረም፤ ለዋሽንግተን ፖስትም ይህንኑ ደጋግመን ነግረናቸዋል" ያሉት ፕሬስ ሴክሬታሪዋ፣ በመቀጠልም ትራምፕ "ሚኒስትሩን እንደሚወዷቸው እና እጅግ አስደናቂ ስራ እየሰሩ እንደሆነ እንደሚያስቡ" አክለው ገልጸዋል።
1 day ago
ግብፅ ኢትዮጵያ በዓባይ ወንዝ ላይ ተጨማሪ ግድቦችን እንድትገነባ «አልፈቅድም» ስትል አስጠነቀቀች
ግብፅ ኢትዮጵያ በዓባይ (ብሉ ናይል) ወንዝ ላይ ተጨማሪ የውሃ ግድቦችን እንድትገነባ በፍፁም የማትፈቅድ መሆኑን የሀገሪቱ የውሃ ሀብት እና መስኖ ሚኒስትር ሀኒ ሴዊላም አስታወቁ። ሚኒስትሩ ይፋዊ መግለጫ የሰጡት ኢትዮጵያ በወንዙ ላይ ተጨማሪ የሃይድሮ ኤሌክትሪክ ማመንጫ ፕሮጀክቶችን ልትገነባ ነው መባሉን ተከተሎ ካይሮ በውሃ ደህንነቷ ላይ ያደገባትን ስጋት በድጋሚ ባንጸባረቀችበት ወቅት ነው።
ሚኒስትር ሀኒ ሴዊላም በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ፣ ኢትዮጵያ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን ጨምሮ በአጠቃላይ አራት ግድቦችን በወንዙ ላይ ለመገንባት ያወጣችው እቅድ አዲስ አለመሆኑን እና ግብፅ ቀደሞውኑ የምታውቀው ጉዳይ መሆኑን ገልጸዋል። ሆኖም «የግብፅ መንግስት እነዚህ ተጨማሪ ፕሮጀክቶች ወደፊት እንዲገፉ እና እንዲተገበሩ ይፈቅዳል ወይ? መልሱ አይሆንም ነው» ሲሉ ካይሮ የተፋሰሱን የታችኛ ሀገራት መብት የማይጠብቅ እና ህጋዊ አሰሪ ውል የሌለውን ማንኛውንም ተቋም አጥብቃ የምትቃወም መሆኗን አረጋግጠዋል።
በሌላ በኩል ሚኒስትሩ ወቅታዊውን የአባይ ወንዝ የውሃ ፍሰት አስመልክተው በሰጡት ማብራሪያ፣ እስከ ነሐሴ ወር መጀመሪያ ድረስ ከኢትዮጵያ ከፍተኛ ቦታዎች ወደ ግብፅ የሚፈሰው የውሃ መጠን ከመደበኛው ወቅታዊ አማካይ መጠን በጥቂቱ ዝቅተኛ መሆኑን ተናግረዋል። ሆኖም በኢትዮጵያ ደጋማ ቦታዎች ያለው የዝናብ ወቅት ገና በጅምር ላይ ያለ እና እስከ ነሐሴ እና መስከረም ወራት ድረስ የሚቀጥል በመሆኑ ሁኔታው የከፋ ድርቅ መከሰቱን የሚያሳይ አይደለም ሲሉ አብራርተዋል።
ግብፅ የሀገሪቱን የውሃ ደህንነት ለማስጠበቅ የዓባይ ወንዝ የጎርፍ ሁኔታን፣ የዝናብ ስርጭትን እና የውሃ ፍሰቱን በላቀ የሳተላይት እና የሃይድሮሎጂ መረጃ መከታተያ ስርአት በየዕለቱ እየተከታተለች መሆኗንም ሚኒስትሩ አክለው ገልጸዋል።
Seledadotio
Seledadotio
ግብፅ ኢትዮጵያ በዓባይ (ብሉ ናይል) ወንዝ ላይ ተጨማሪ የውሃ ግድቦችን እንድትገነባ በፍፁም የማትፈቅድ መሆኑን የሀገሪቱ የውሃ ሀብት እና መስኖ ሚኒስትር ሀኒ ሴዊላም አስታወቁ። ሚኒስትሩ ይፋዊ መግለጫ የሰጡት ኢትዮጵያ በወንዙ ላይ ተጨማሪ የሃይድሮ ኤሌክትሪክ ማመንጫ ፕሮጀክቶችን ልትገነባ ነው መባሉን ተከተሎ ካይሮ በውሃ ደህንነቷ ላይ ያደገባትን ስጋት በድጋሚ ባንጸባረቀችበት ወቅት ነው።
ሚኒስትር ሀኒ ሴዊላም በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ፣ ኢትዮጵያ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን ጨምሮ በአጠቃላይ አራት ግድቦችን በወንዙ ላይ ለመገንባት ያወጣችው እቅድ አዲስ አለመሆኑን እና ግብፅ ቀደሞውኑ የምታውቀው ጉዳይ መሆኑን ገልጸዋል። ሆኖም «የግብፅ መንግስት እነዚህ ተጨማሪ ፕሮጀክቶች ወደፊት እንዲገፉ እና እንዲተገበሩ ይፈቅዳል ወይ? መልሱ አይሆንም ነው» ሲሉ ካይሮ የተፋሰሱን የታችኛ ሀገራት መብት የማይጠብቅ እና ህጋዊ አሰሪ ውል የሌለውን ማንኛውንም ተቋም አጥብቃ የምትቃወም መሆኗን አረጋግጠዋል።
በሌላ በኩል ሚኒስትሩ ወቅታዊውን የአባይ ወንዝ የውሃ ፍሰት አስመልክተው በሰጡት ማብራሪያ፣ እስከ ነሐሴ ወር መጀመሪያ ድረስ ከኢትዮጵያ ከፍተኛ ቦታዎች ወደ ግብፅ የሚፈሰው የውሃ መጠን ከመደበኛው ወቅታዊ አማካይ መጠን በጥቂቱ ዝቅተኛ መሆኑን ተናግረዋል። ሆኖም በኢትዮጵያ ደጋማ ቦታዎች ያለው የዝናብ ወቅት ገና በጅምር ላይ ያለ እና እስከ ነሐሴ እና መስከረም ወራት ድረስ የሚቀጥል በመሆኑ ሁኔታው የከፋ ድርቅ መከሰቱን የሚያሳይ አይደለም ሲሉ አብራርተዋል።
ግብፅ የሀገሪቱን የውሃ ደህንነት ለማስጠበቅ የዓባይ ወንዝ የጎርፍ ሁኔታን፣ የዝናብ ስርጭትን እና የውሃ ፍሰቱን በላቀ የሳተላይት እና የሃይድሮሎጂ መረጃ መከታተያ ስርአት በየዕለቱ እየተከታተለች መሆኗንም ሚኒስትሩ አክለው ገልጸዋል።
Seledadotio
Seledadotio
2 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) ኢትዮጵያ ለግማሽ ምዕተ ዓመት ገደማ የውጭ ባንኮች በሀገሪቱ የፋይናንስ ዘርፍ ውስጥ እንዳይገቡ የጣለችውን እገዳ አንስታለች። በሰኔ 2025 በወጣው ታሪካዊ መመሪያ መሰረት፣ ዓለም አቀፍ አበዳሪዎች ቅርንጫፎችን መክፈት፣ የራሳቸውን ተቋም ማቋቋም እና በልዩ ሁኔታዎች የሀገር ውስጥ ባንኮችን ሙሉ በሙሉ መግዛት የሚችሉበት ዕድል ተፈጥሯል። ይሁን እንጂ ውሳኔው ከተላለፈ ከአንድ ዓመት በኋላ፣ የአፍሪካ ግዙፍ ባንኮች ከፍተኛ ፍላጎት ቢያሳዩም እስካሁን በተግባር ወደ ገበያው የገባ የውጭ ባንክ የለም።
ይህ ታሪካዊ እርምጃ የጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ የሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ አጀንዳ አካል ነው። የባንክ ስራ አዋጅ ቁጥር 1360/2024 በታህሳስ 2024 በፓርላማ ፀድቆ በመጋቢት 2025 በነጋሪት ጋዜጣ ታትሟል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክም በሰኔ 2025 የውጭ ባንኮችን የፍቃድ አሰጣጥ የሚገዛውን መመሪያ ይፋ አድርጓል።
መመሪያው የውጭ ባንኮች ወደ ገበያው የሚገቡባቸውን አምስት መንገዶች ቢያስቀምጥም፣ ጥብቅ የባለቤትነት ገደቦችን አስቀምጧል። በአንድ ባንክ ውስጥ የውጭ ዜጎች አጠቃላይ የባለቤትነት ድርሻ ከ49 በመቶ መብለጥ አይችልም። አንድ ስትራቴጂካዊ የውጭ ባለሀብት እስከ 40 በመቶ ብቻ መያዝ ሲችል፣ የውጭ ኩባንያዎች እስከ 10 በመቶ፣ እንዲሁም ግለሰቦች እስከ 7 በመቶ ድርሻ ብቻ ሊኖራቸው ይችላል። በተጨማሪም ማንኛውም የውጭ ባንክ ቅርንጫፍ ወይም ተቋም ሲያቋቁም ቢያንስ 5 ቢሊዮን ብር (በወቅቱ የምንዛሬ ተመን 32 ሚሊዮን ዶላር) የተከፈለ ካፒታል በውጭ ምንዛሬ እና በጥሬ ገንዘብ (በተዘዋዋሪ ክፍያ ሳይሆን) ማምጣት ይጠበቅበታል።
እስካሁን ቢያንስ ሰባት ትልልቅ የአፍሪካ ባንኮች ወደ ኢትዮጵያ ገበያ የመግባት ፍላጎት አሳይተዋል። በጠቅላላ ሀብቱ በአፍሪካ ትልቁ ባንክ የሆነው ስታንዳርድ ባንክ ግሩፕ፣ በህዳር 2025 በአዲሱ ማዕቀፍ መሰረት የውክልና ቢሮውን ፈቃድ ያደሰ የመጀመሪያው የውጭ ተቋም ሲሆን፣ አሁን ላይ ከባዶ የራሱን ባንክ ስለማቋቋም እያሰበ ይገኛል። የምስራቅ አፍሪካው ግዙፍ አበዳሪ ኬሲቢ ግሩፕ በ2026 መገባደጃ ላይ ሙሉ በሙሉ ወደ ገበያው ለመግባት እያለመ ሲሆን፣ ለዚህም ከሀገር ውስጥ አጋር ጋር አብሮ ለመስራት እያፈላለገ ይገኛል።
በተመሳሳይ የኬንያው ከፍተኛ ትርፋማ ባንክ ኢኩዊቲ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈፃሚ ከመንግስት የኢንቨስትመንት ኮሚሽን ጋር በሴፕቴምበር 2025 ቀጥተኛ ውይይት አድርገዋል። ከነዚህም በተጨማሪ እንደ የደቡብ አፍሪካው አብሳ፣ የጅቡቲው ቢሲአይኤምአር፣ እንዲሁም የናይጄሪያዎቹ ዜኒዝ እና ፈርስት ባንክ ገበያውን እና አማራጮችን በማጥናት ላይ እንደሚገኙ ታውቋል።
በባንኮቹ በኩል ከፍተኛ ፍላጎት ቢኖርም እስካሁን በተግባር ወደ ስራ ያልገቡባቸው ዋና ዋና ምክንያቶች አሉ። የመጀመሪያው ጉዳይ የ49 በመቶው የባለቤትነት ድርሻ ገደብ ነው። አብዛኛዎቹ የውጭ ባንኮች አዲስ ገበያ ሲገቡ የአብላጫ ድርሻ መያዝ ይፈልጋሉ። ነገር ግን ይህ ገደብ በስትራቴጂ፣ በአስተዳደር እና በካፒታል ድልድል ላይ ያላቸውን ውሳኔ ሰጪነት ስለሚገድበው አንዳንዶቹን የባለቤትነት ጣራው እስኪሻሻል እንዲያመነቱ አድርጓቸዋል።
ቀጣዩ ምክንያት የውጭ ምንዛሬ እና የዕዳ ስጋት ነው። መንግስት የውጭ ምንዛሬ ተመኑን በገበያ እንዲወሰን ማድረጉ በጎ እርምጃ ቢሆንም፣ ኢትዮጵያ በታህሳስ 2023 የ1 ቢሊዮን ዶላር የዩሮቦንድ እዳዋን መክፈል አለመቻሏ እና ያላት አነስተኛ የውጭ ምንዛሬ ክምችት የውጭ ባንኮችን አሳስቧል። እነዚህ ባንኮች ትርፋቸውን በውጭ ምንዛሬ ወደ ሀገራቸው ይዘው መውጣት ስለመቻላቸው እርግጠኛ መሆን ይፈልጋሉ።
በመጨረሻም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የውጭ ባንኮችን በፍጥነት ከማስገባት ይልቅ በመጀመሪያ የሀገር ውስጥ ባንኮችን አቅም ለማጠናከር ትኩረት መስጠቱ ለዘገየው ሒደት ሌላኛው ምክንያት ነው። የባንኮች ዝቅተኛ የተከፈለ ካፒታል ወደ 5 ቢሊዮን ብር ከፍ እንዲል በማድረግ ባንኮች አቅማቸውን እንዲያጎለብቱ ወይም እንዲዋሃዱ ግፊት እያደረገ ነው። ከዚህ ጋር ተያይዞ በቅርቡ ስራ የጀመረው የኢትዮጵያ ሰነደ ሙአለነዋይ ገበያ ለሀገር ውስጥ ባንኮች ተጨማሪ ካፒታል የማሰባሰቢያ መድረክ ሆኖላቸዋል።
እስካሁን የውጭ ባንክ ፈቃድ አለመሰጠቱ የሪፎርሙን ውድቀት አያሳይም፤ ይልቁንም የሽግግሩ ሂደት ከመጀመሪያው የዜና ጩኸት ይልቅ በተረጋጋ እና በጥንቃቄ እየሄደ መሆኑን ያመላክታል። ትልቁ ጥያቄ ያለው የኢትዮጵያ መንግስት በቀጣይ በባለቤትነት ገደቦች፣ በካፒታል እና በውጭ ምንዛሬ አቅርቦት ዙሪያ ያሉትን ጥብቅ ደንቦች ምን ያህል ያላግባቸዋል በሚለው ላይ የተመሰረተ ነው።
ይህ ታሪካዊ እርምጃ የጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ የሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ አጀንዳ አካል ነው። የባንክ ስራ አዋጅ ቁጥር 1360/2024 በታህሳስ 2024 በፓርላማ ፀድቆ በመጋቢት 2025 በነጋሪት ጋዜጣ ታትሟል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክም በሰኔ 2025 የውጭ ባንኮችን የፍቃድ አሰጣጥ የሚገዛውን መመሪያ ይፋ አድርጓል።
መመሪያው የውጭ ባንኮች ወደ ገበያው የሚገቡባቸውን አምስት መንገዶች ቢያስቀምጥም፣ ጥብቅ የባለቤትነት ገደቦችን አስቀምጧል። በአንድ ባንክ ውስጥ የውጭ ዜጎች አጠቃላይ የባለቤትነት ድርሻ ከ49 በመቶ መብለጥ አይችልም። አንድ ስትራቴጂካዊ የውጭ ባለሀብት እስከ 40 በመቶ ብቻ መያዝ ሲችል፣ የውጭ ኩባንያዎች እስከ 10 በመቶ፣ እንዲሁም ግለሰቦች እስከ 7 በመቶ ድርሻ ብቻ ሊኖራቸው ይችላል። በተጨማሪም ማንኛውም የውጭ ባንክ ቅርንጫፍ ወይም ተቋም ሲያቋቁም ቢያንስ 5 ቢሊዮን ብር (በወቅቱ የምንዛሬ ተመን 32 ሚሊዮን ዶላር) የተከፈለ ካፒታል በውጭ ምንዛሬ እና በጥሬ ገንዘብ (በተዘዋዋሪ ክፍያ ሳይሆን) ማምጣት ይጠበቅበታል።
እስካሁን ቢያንስ ሰባት ትልልቅ የአፍሪካ ባንኮች ወደ ኢትዮጵያ ገበያ የመግባት ፍላጎት አሳይተዋል። በጠቅላላ ሀብቱ በአፍሪካ ትልቁ ባንክ የሆነው ስታንዳርድ ባንክ ግሩፕ፣ በህዳር 2025 በአዲሱ ማዕቀፍ መሰረት የውክልና ቢሮውን ፈቃድ ያደሰ የመጀመሪያው የውጭ ተቋም ሲሆን፣ አሁን ላይ ከባዶ የራሱን ባንክ ስለማቋቋም እያሰበ ይገኛል። የምስራቅ አፍሪካው ግዙፍ አበዳሪ ኬሲቢ ግሩፕ በ2026 መገባደጃ ላይ ሙሉ በሙሉ ወደ ገበያው ለመግባት እያለመ ሲሆን፣ ለዚህም ከሀገር ውስጥ አጋር ጋር አብሮ ለመስራት እያፈላለገ ይገኛል።
በተመሳሳይ የኬንያው ከፍተኛ ትርፋማ ባንክ ኢኩዊቲ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈፃሚ ከመንግስት የኢንቨስትመንት ኮሚሽን ጋር በሴፕቴምበር 2025 ቀጥተኛ ውይይት አድርገዋል። ከነዚህም በተጨማሪ እንደ የደቡብ አፍሪካው አብሳ፣ የጅቡቲው ቢሲአይኤምአር፣ እንዲሁም የናይጄሪያዎቹ ዜኒዝ እና ፈርስት ባንክ ገበያውን እና አማራጮችን በማጥናት ላይ እንደሚገኙ ታውቋል።
በባንኮቹ በኩል ከፍተኛ ፍላጎት ቢኖርም እስካሁን በተግባር ወደ ስራ ያልገቡባቸው ዋና ዋና ምክንያቶች አሉ። የመጀመሪያው ጉዳይ የ49 በመቶው የባለቤትነት ድርሻ ገደብ ነው። አብዛኛዎቹ የውጭ ባንኮች አዲስ ገበያ ሲገቡ የአብላጫ ድርሻ መያዝ ይፈልጋሉ። ነገር ግን ይህ ገደብ በስትራቴጂ፣ በአስተዳደር እና በካፒታል ድልድል ላይ ያላቸውን ውሳኔ ሰጪነት ስለሚገድበው አንዳንዶቹን የባለቤትነት ጣራው እስኪሻሻል እንዲያመነቱ አድርጓቸዋል።
ቀጣዩ ምክንያት የውጭ ምንዛሬ እና የዕዳ ስጋት ነው። መንግስት የውጭ ምንዛሬ ተመኑን በገበያ እንዲወሰን ማድረጉ በጎ እርምጃ ቢሆንም፣ ኢትዮጵያ በታህሳስ 2023 የ1 ቢሊዮን ዶላር የዩሮቦንድ እዳዋን መክፈል አለመቻሏ እና ያላት አነስተኛ የውጭ ምንዛሬ ክምችት የውጭ ባንኮችን አሳስቧል። እነዚህ ባንኮች ትርፋቸውን በውጭ ምንዛሬ ወደ ሀገራቸው ይዘው መውጣት ስለመቻላቸው እርግጠኛ መሆን ይፈልጋሉ።
በመጨረሻም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የውጭ ባንኮችን በፍጥነት ከማስገባት ይልቅ በመጀመሪያ የሀገር ውስጥ ባንኮችን አቅም ለማጠናከር ትኩረት መስጠቱ ለዘገየው ሒደት ሌላኛው ምክንያት ነው። የባንኮች ዝቅተኛ የተከፈለ ካፒታል ወደ 5 ቢሊዮን ብር ከፍ እንዲል በማድረግ ባንኮች አቅማቸውን እንዲያጎለብቱ ወይም እንዲዋሃዱ ግፊት እያደረገ ነው። ከዚህ ጋር ተያይዞ በቅርቡ ስራ የጀመረው የኢትዮጵያ ሰነደ ሙአለነዋይ ገበያ ለሀገር ውስጥ ባንኮች ተጨማሪ ካፒታል የማሰባሰቢያ መድረክ ሆኖላቸዋል።
እስካሁን የውጭ ባንክ ፈቃድ አለመሰጠቱ የሪፎርሙን ውድቀት አያሳይም፤ ይልቁንም የሽግግሩ ሂደት ከመጀመሪያው የዜና ጩኸት ይልቅ በተረጋጋ እና በጥንቃቄ እየሄደ መሆኑን ያመላክታል። ትልቁ ጥያቄ ያለው የኢትዮጵያ መንግስት በቀጣይ በባለቤትነት ገደቦች፣ በካፒታል እና በውጭ ምንዛሬ አቅርቦት ዙሪያ ያሉትን ጥብቅ ደንቦች ምን ያህል ያላግባቸዋል በሚለው ላይ የተመሰረተ ነው።
2 days ago
ግብፅ ኢትዮጵያ በዓባይ ወንዝ ላይ ተጨማሪ ግድቦችን እንድትገነባ «አልፈቅድም» ስትል አስጠነቀቀች
#fastmereja I ግብፅ ኢትዮጵያ በዓባይ (ብሉ ናይል) ወንዝ ላይ ተጨማሪ የውሃ ግድቦችን እንድትገነባ በፍፁም የማትፈቅድ መሆኑን የሀገሪቱ የውሃ ሀብት እና መስኖ ሚኒስትር ሀኒ ሴዊላም አስታወቁ። ሚኒስትሩ ይፋዊ መግለጫ የሰጡት ኢትዮጵያ በወንዙ ላይ ተጨማሪ የሃይድሮ ኤሌክትሪክ ማመንጫ ፕሮጀክቶችን ልትገነባ ነው መባሉን ተከተሎ ካይሮ በውሃ ደህንነቷ ላይ ያደገባትን ስጋት በድጋሚ ባንጸባረቀችበት ወቅት ነው።
ሚኒስትር ሀኒ ሴዊላም በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ፣ ኢትዮጵያ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን ጨምሮ በአጠቃላይ አራት ግድቦችን በወንዙ ላይ ለመገንባት ያወጣችው እቅድ አዲስ አለመሆኑን እና ግብፅ ቀደሞውኑ የምታውቀው ጉዳይ መሆኑን ገልጸዋል። ሆኖም «የግብፅ መንግስት እነዚህ ተጨማሪ ፕሮጀክቶች ወደፊት እንዲገፉ እና እንዲተገበሩ ይፈቅዳል ወይ? መልሱ አይሆንም ነው» ሲሉ ካይሮ የተፋሰሱን የታችኛ ሀገራት መብት የማይጠብቅ እና ህጋዊ አሰሪ ውል የሌለውን ማንኛውንም ተቋም አጥብቃ የምትቃወም መሆኗን አረጋግጠዋል።
በሌላ በኩል ሚኒስትሩ ወቅታዊውን የአባይ ወንዝ የውሃ ፍሰት አስመልክተው በሰጡት ማብራሪያ፣ እስከ ነሐሴ ወር መጀመሪያ ድረስ ከኢትዮጵያ ከፍተኛ ቦታዎች ወደ ግብፅ የሚፈሰው የውሃ መጠን ከመደበኛው ወቅታዊ አማካይ መጠን በጥቂቱ ዝቅተኛ መሆኑን ተናግረዋል። ሆኖም በኢትዮጵያ ደጋማ ቦታዎች ያለው የዝናብ ወቅት ገና በጅምር ላይ ያለ እና እስከ ነሐሴ እና መስከረም ወራት ድረስ የሚቀጥል በመሆኑ ሁኔታው የከፋ ድርቅ መከሰቱን የሚያሳይ አይደለም ሲሉ አብራርተዋል።
ግብፅ የሀገሪቱን የውሃ ደህንነት ለማስጠበቅ የዓባይ ወንዝ የጎርፍ ሁኔታን፣ የዝናብ ስርጭትን እና የውሃ ፍሰቱን በላቀ የሳተላይት እና የሃይድሮሎጂ መረጃ መከታተያ ስርአት በየዕለቱ እየተከታተለች መሆኗንም ሚኒስትሩ አክለው ገልጸዋል።
#fastmereja I ግብፅ ኢትዮጵያ በዓባይ (ብሉ ናይል) ወንዝ ላይ ተጨማሪ የውሃ ግድቦችን እንድትገነባ በፍፁም የማትፈቅድ መሆኑን የሀገሪቱ የውሃ ሀብት እና መስኖ ሚኒስትር ሀኒ ሴዊላም አስታወቁ። ሚኒስትሩ ይፋዊ መግለጫ የሰጡት ኢትዮጵያ በወንዙ ላይ ተጨማሪ የሃይድሮ ኤሌክትሪክ ማመንጫ ፕሮጀክቶችን ልትገነባ ነው መባሉን ተከተሎ ካይሮ በውሃ ደህንነቷ ላይ ያደገባትን ስጋት በድጋሚ ባንጸባረቀችበት ወቅት ነው።
ሚኒስትር ሀኒ ሴዊላም በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ፣ ኢትዮጵያ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን ጨምሮ በአጠቃላይ አራት ግድቦችን በወንዙ ላይ ለመገንባት ያወጣችው እቅድ አዲስ አለመሆኑን እና ግብፅ ቀደሞውኑ የምታውቀው ጉዳይ መሆኑን ገልጸዋል። ሆኖም «የግብፅ መንግስት እነዚህ ተጨማሪ ፕሮጀክቶች ወደፊት እንዲገፉ እና እንዲተገበሩ ይፈቅዳል ወይ? መልሱ አይሆንም ነው» ሲሉ ካይሮ የተፋሰሱን የታችኛ ሀገራት መብት የማይጠብቅ እና ህጋዊ አሰሪ ውል የሌለውን ማንኛውንም ተቋም አጥብቃ የምትቃወም መሆኗን አረጋግጠዋል።
በሌላ በኩል ሚኒስትሩ ወቅታዊውን የአባይ ወንዝ የውሃ ፍሰት አስመልክተው በሰጡት ማብራሪያ፣ እስከ ነሐሴ ወር መጀመሪያ ድረስ ከኢትዮጵያ ከፍተኛ ቦታዎች ወደ ግብፅ የሚፈሰው የውሃ መጠን ከመደበኛው ወቅታዊ አማካይ መጠን በጥቂቱ ዝቅተኛ መሆኑን ተናግረዋል። ሆኖም በኢትዮጵያ ደጋማ ቦታዎች ያለው የዝናብ ወቅት ገና በጅምር ላይ ያለ እና እስከ ነሐሴ እና መስከረም ወራት ድረስ የሚቀጥል በመሆኑ ሁኔታው የከፋ ድርቅ መከሰቱን የሚያሳይ አይደለም ሲሉ አብራርተዋል።
ግብፅ የሀገሪቱን የውሃ ደህንነት ለማስጠበቅ የዓባይ ወንዝ የጎርፍ ሁኔታን፣ የዝናብ ስርጭትን እና የውሃ ፍሰቱን በላቀ የሳተላይት እና የሃይድሮሎጂ መረጃ መከታተያ ስርአት በየዕለቱ እየተከታተለች መሆኗንም ሚኒስትሩ አክለው ገልጸዋል።
2 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የግብፁ የመስኖ ሚኒስትር ሀኒ ስዊላም ኢትዮጵያ በአባይ ወንዝ ላይ አዳዲስ ግድቦችን እንድትገነባ ሀገራቸው እንደማትፈቅድ አስታወቁ። ይህ የግብፅ ማስጠንቀቂያ የተሰማው፣ ኢትዮጵያ ከታላቁ ህዳሴ ግድብ በተጨማሪ ሌሎች ሶስት አዳዲስ ግድቦችን በአባይ ወንዝ ላይ ለመገንባት ማቀዷን የሚገልጹ ዘገባዎች ከወጡ ከሁለት ሳምንታት በኋላ ነው። ሚኒስትሩ በካይሮ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ "ኢትዮጵያ አዳዲስ ግድቦችን የመገንባት እቅድ እንዳላት በደንብ ይታወቃል፤ ነገር ግን የግብፅ መንግስት ይህንን ይፈቅዳል ወይ? አይፈቅድም" ሲሉ በፅኑ ተናግረዋል።
አክለውም የታችኛው ተፋሰስ ሀገራት የሆኑት ግብፅ እና ሱዳን የሚለቀቀውን የውሃ መጠን እና ዓመታዊ የክንውን እቅዶችን ማወቅ እንዲችሉ፣ የህዳሴ ግድቡን የውሃ ሙሌት እና ኦፕሬሽን መረጃ ለመለዋወጥ የሚያስችል ግልፅ እና ህጋዊ አስገዳጅነት ያለው ስምምነት እንዲኖር ግብፅ ደጋግማ ስትጠይቅ መቆየቷን አስገንዝበዋል። የዚህ አይነት የመረጃ ልውውጥ አለመኖር ሱዳንን እጅግ አሳሳቢ ሁኔታ ውስጥ እንደሚከታት ሚኒስትሩ ገልፀዋል። ከኢትዮጵያ የሚለቀቀውን የውሃ መጠን እና ጊዜ በተመለከተ ትክክለኛ መረጃ ባለመኖሩ፣ የሱዳን ባለስልጣናት የራሳቸውን ግድቦች በአግባቡ ማስተዳደርም ሆነ ውሃ ማጠራቀም ተስኗቸዋል ብለዋል። በዚህም መሰረት ለውሃ አስተዳደሩ መስተጓጎል ሱዳን ልትወቀስ አይገባትም ያሉት ሀኒ ስዊላም፣ መረጃ ለመለዋወጥ እና ከታችኛው ተፋሰስ ሀገራት ጋር በቅንጅት ለመስራት የሚያስችል ህጋዊ አስገዳጅ ስምምነት ላይ ለመድረስ ፈቃደኛ ባለመሆኗ ሙሉ ኃላፊነቱን የምትወስደው ኢትዮጵያ ናት ሲሉ ወቅሰዋል።
የግብፅ መንግስት የሁሉንም ወገኖች ጥቅም በሚያስጠብቅ እና የጋራ የውሃ ሀብትን በማስተዳደር ሂደት ሊከሰቱ የሚችሉ አደጋዎችን በሚቀንስ መልኩ መደበኛ የመረጃ ልውውጥን የሚያረጋግጥ ህጋዊ አስገዳጅነት ያለው ስምምነት ላይ ለመድረስ አሁንም ቁርጠኛ መሆኑን ሚኒስትሩ አረጋግጠዋል። ለግብፅ ባለስልጣን ንግግር ከኢትዮጵያ በኩል እስካሁን የተሰጠ ምላሽ የለም።
እ.ኤ.አ በ2011 ግንባታው የጀመረውን የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን ሙሌት እና አስተዳደር በተመለከተ ግብፅ እና ሱዳን ከኢትዮጵያ ጋር ለረጅም ጊዜ ውዝግብ ውስጥ መቆየታቸው ይታወቃል። ካይሮ እና ካርቱም ግድቡ ሙሉ በሙሉ ስራ ከመጀመሩ በፊት የሶስትዮሽ አስገዳጅ ህጋዊ ስምምነት ሊኖር ይገባል ብለው ሲያምኑ፣ ኢትዮጵያ በበኩሏ ግድቡ የታችኛውን ተፋሰስ ሀገራት እንደማይጎዳ በመግለጽ እንዲህ አይነት አስገዳጅ ስምምነት አያስፈልግም የሚል ፅኑ አቋም ታራምዳለች። በመሆኑም በጉዳዩ ዙሪያ ሲደረግ የነበረው ድርድር ለሶስት ዓመታት ተቋርጦ በ2023 ዳግም ቢጀመርም፣ በ2024 እንደገና ያለ ስምምነት መቋረጡ ይታወሳል። ስድስት ሺህ ስድስት መቶ ሃምሳ ኪሎ ሜትር የሚረዝመው የአባይ ወንዝ፣ ኢትዮጵያ፣ ሱዳን እና ግብፅን ጨምሮ በ11 የአፍሪካ ሀገራት የሚያቋርጥ ግዙፍ የውሃ ሀብት ነው።
አክለውም የታችኛው ተፋሰስ ሀገራት የሆኑት ግብፅ እና ሱዳን የሚለቀቀውን የውሃ መጠን እና ዓመታዊ የክንውን እቅዶችን ማወቅ እንዲችሉ፣ የህዳሴ ግድቡን የውሃ ሙሌት እና ኦፕሬሽን መረጃ ለመለዋወጥ የሚያስችል ግልፅ እና ህጋዊ አስገዳጅነት ያለው ስምምነት እንዲኖር ግብፅ ደጋግማ ስትጠይቅ መቆየቷን አስገንዝበዋል። የዚህ አይነት የመረጃ ልውውጥ አለመኖር ሱዳንን እጅግ አሳሳቢ ሁኔታ ውስጥ እንደሚከታት ሚኒስትሩ ገልፀዋል። ከኢትዮጵያ የሚለቀቀውን የውሃ መጠን እና ጊዜ በተመለከተ ትክክለኛ መረጃ ባለመኖሩ፣ የሱዳን ባለስልጣናት የራሳቸውን ግድቦች በአግባቡ ማስተዳደርም ሆነ ውሃ ማጠራቀም ተስኗቸዋል ብለዋል። በዚህም መሰረት ለውሃ አስተዳደሩ መስተጓጎል ሱዳን ልትወቀስ አይገባትም ያሉት ሀኒ ስዊላም፣ መረጃ ለመለዋወጥ እና ከታችኛው ተፋሰስ ሀገራት ጋር በቅንጅት ለመስራት የሚያስችል ህጋዊ አስገዳጅ ስምምነት ላይ ለመድረስ ፈቃደኛ ባለመሆኗ ሙሉ ኃላፊነቱን የምትወስደው ኢትዮጵያ ናት ሲሉ ወቅሰዋል።
የግብፅ መንግስት የሁሉንም ወገኖች ጥቅም በሚያስጠብቅ እና የጋራ የውሃ ሀብትን በማስተዳደር ሂደት ሊከሰቱ የሚችሉ አደጋዎችን በሚቀንስ መልኩ መደበኛ የመረጃ ልውውጥን የሚያረጋግጥ ህጋዊ አስገዳጅነት ያለው ስምምነት ላይ ለመድረስ አሁንም ቁርጠኛ መሆኑን ሚኒስትሩ አረጋግጠዋል። ለግብፅ ባለስልጣን ንግግር ከኢትዮጵያ በኩል እስካሁን የተሰጠ ምላሽ የለም።
እ.ኤ.አ በ2011 ግንባታው የጀመረውን የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን ሙሌት እና አስተዳደር በተመለከተ ግብፅ እና ሱዳን ከኢትዮጵያ ጋር ለረጅም ጊዜ ውዝግብ ውስጥ መቆየታቸው ይታወቃል። ካይሮ እና ካርቱም ግድቡ ሙሉ በሙሉ ስራ ከመጀመሩ በፊት የሶስትዮሽ አስገዳጅ ህጋዊ ስምምነት ሊኖር ይገባል ብለው ሲያምኑ፣ ኢትዮጵያ በበኩሏ ግድቡ የታችኛውን ተፋሰስ ሀገራት እንደማይጎዳ በመግለጽ እንዲህ አይነት አስገዳጅ ስምምነት አያስፈልግም የሚል ፅኑ አቋም ታራምዳለች። በመሆኑም በጉዳዩ ዙሪያ ሲደረግ የነበረው ድርድር ለሶስት ዓመታት ተቋርጦ በ2023 ዳግም ቢጀመርም፣ በ2024 እንደገና ያለ ስምምነት መቋረጡ ይታወሳል። ስድስት ሺህ ስድስት መቶ ሃምሳ ኪሎ ሜትር የሚረዝመው የአባይ ወንዝ፣ ኢትዮጵያ፣ ሱዳን እና ግብፅን ጨምሮ በ11 የአፍሪካ ሀገራት የሚያቋርጥ ግዙፍ የውሃ ሀብት ነው።
Sponsored by
Surafel
3 days ago
ብሩስ ዊሊስ ባለቤት የባለቤቷን ህመም (FTD) ለመከታተል የሚያስችል ህግ እንዲፀድቅ ግፊት አደረገች
የታዋቂው የፊልም ኮከብ ብሩስ ዊሊስ ባለቤት የሆነችው ኤማ ሄሚንግ ዊሊስ፣ ባለቤቷ የተጠቃበትን 'የፊት ለፊት የጭንቅላት ክፍል መጎዳት' (Frontotemporal Degeneration - FTD) የተሰኘውን የመርሳት ህመም የሚከታተል ህግ እንዲፀድቅ ሰኞ ዕለት በካሊፎርኒያ ካፒቶል ከሚገኙ ህግ አውጪዎች ጋር በመሆን ግፊት አድርጋለች።
በሴናተር ሮጀር ኒየሎ የተዘጋጀው እና ኤማ ሄሚንግ ዊሊስ ድጋፏን የሰጠችለት ይህ ረቂቅ ህግ፣ የካሊፎርኒያ የህዝብ ጤና መምሪያ ስለ FTD ህመም መረጃዎችን እንዲሰበስብ የሚያስገድድ ነው። መምሪያው በአሁኑ ወቅት የሃንቲንግተን፣ የፓርኪንሰንስ፣ የአልዛይመርስ እና የማልቲፕል ስክለሮሲስ በሽታዎችን መረጃዎች በመሰብሰብ ላይ ይገኛል። የህጉን ሂደት በተመለከተ፣ ረቂቅ ህጉ ሀምሌ 1 ቀን የህግ አውጪው ምክር ቤት የአንድ ወር የክረምት እረፍት ከመውጣቱ በፊት በምክር ቤቱ ተጠባባቂ መዝገብ ውስጥ ሰፍሮ ነበር። ምክር ቤቱ ሰኞ ዕለት ስራውን የጀመረ ሲሆን፣ ረቂቅ ህጎችን ለማጽደቅ የአንድ ወር ጊዜ ብቻ ቀርቶታል። ይህ የህግ ማዕቀፍ እስከ ጥር 1፣ 2032 ድረስ የሚራዘም ሲሆን፣ የህጉ ትንታኔ እንደሚያሳየው ለሰራተኞች እና ለኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ክፍያን ጨምሮ በዓመት 2.7 ሚሊዮን ዶላር በጀት ይጠይቃል።
ኤማ ሰኞ ዕለት በካፒቶል በሰጠችው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ እንዳብራራችው፣ FTDን በነርቭ መጎዳት በሽታዎች መዝገብ ውስጥ ማካተት የካሊፎርኒያ ታካሚዎችን መቁጠር ብቻ ሳይሆን፣ በካሊፎርኒያ የሚገኙ የባዮቴክ ተመራማሪዎች ህክምና እና ፈውስ ለማግኘት የሚፈልጉትን ጠቃሚ የመረጃ ቋት መገንባት ነው። ባለቤቷ ለመጀመሪያ ጊዜ በ2022 በበሽታው መያዙ እንደታወቀ የጠቀሰችው ኤማ፣ አሁን ላይ ህመሙን የሚያዘገይ ወይም የሚያቆም ህክምና እንደሌለ ብታምንም፣ የህመሙን መረጃዎች መሰብሰብ ግን ለምርምር ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳለው ተናግራለች። ታዋቂው ተዋናይ ስለሚገኝበት ሁኔታ ተጠይቃ ስትመልስም፣ በዚህ እጅግ ጨካኝ በሆነ በሽታ ውስጥ ሆኖ ማድረግ የሚችለውን ያህል በጥሩ ሁኔታ ላይ ይገኛል ብዬ አስባለሁ ስትል ገልጻለች።
'ፒክስ ዲዚዝ' በመባልም የሚታወቀው ይህ ህመም፣ ከግንባር ጀርባ ወይም ከጆሮ አካባቢ ባሉ የጭንቅላት ክፍሎች ላይ በሚከሰት የነርቭ ሴሎች መጎዳት የሚመጣ የጭንቅላት እክል ነው። የበሽታው ምልክቶች የባህሪ እና የስብዕና ለውጥን፣ ስሜት አልባ መሆንን ፣ ውሳኔ የመስጠት፣ የመንቀሳቀስ እና የመናገር ችግርን፣ እንዲሁም ቃላትን የመረዳት አቅም ማጣትን ያካትታሉ።
የኤፍ ቲ ዲ ማህበር የጥብቅና እና የበጎ ፈቃደኞች ተሳትፎ ዳይሬክተር የሆኑት ሜጋን ቡዝቢ እንደገለጹት፣ የታካሚ ቤተሰቦች እነዚህ ምልክቶች ሲታዩ ከሐኪሞች ግልጽ የሆነ ምላሽ ለማግኘት ብዙ ጊዜ ይቸገራሉ። ዳይሬክተሯ አክለውም፣ ይህ ሁኔታ ለብዙ የካሊፎርኒያ ቤተሰቦች የFTD ምርመራ ውጤትን ለማግኘት የሚያደርጉት ረጅም እና አድካሚ ጉዞ እውነታ መሆኑን አብራርተዋል። በአሁኑ ወቅት በሽታውን ለማከም የሚረዱ ህክምናዎች እጅግ ውስን ሲሆኑ፣ ፈውስም እስካሁን አልተገኘለትም።
የታዋቂው የፊልም ኮከብ ብሩስ ዊሊስ ባለቤት የሆነችው ኤማ ሄሚንግ ዊሊስ፣ ባለቤቷ የተጠቃበትን 'የፊት ለፊት የጭንቅላት ክፍል መጎዳት' (Frontotemporal Degeneration - FTD) የተሰኘውን የመርሳት ህመም የሚከታተል ህግ እንዲፀድቅ ሰኞ ዕለት በካሊፎርኒያ ካፒቶል ከሚገኙ ህግ አውጪዎች ጋር በመሆን ግፊት አድርጋለች።
በሴናተር ሮጀር ኒየሎ የተዘጋጀው እና ኤማ ሄሚንግ ዊሊስ ድጋፏን የሰጠችለት ይህ ረቂቅ ህግ፣ የካሊፎርኒያ የህዝብ ጤና መምሪያ ስለ FTD ህመም መረጃዎችን እንዲሰበስብ የሚያስገድድ ነው። መምሪያው በአሁኑ ወቅት የሃንቲንግተን፣ የፓርኪንሰንስ፣ የአልዛይመርስ እና የማልቲፕል ስክለሮሲስ በሽታዎችን መረጃዎች በመሰብሰብ ላይ ይገኛል። የህጉን ሂደት በተመለከተ፣ ረቂቅ ህጉ ሀምሌ 1 ቀን የህግ አውጪው ምክር ቤት የአንድ ወር የክረምት እረፍት ከመውጣቱ በፊት በምክር ቤቱ ተጠባባቂ መዝገብ ውስጥ ሰፍሮ ነበር። ምክር ቤቱ ሰኞ ዕለት ስራውን የጀመረ ሲሆን፣ ረቂቅ ህጎችን ለማጽደቅ የአንድ ወር ጊዜ ብቻ ቀርቶታል። ይህ የህግ ማዕቀፍ እስከ ጥር 1፣ 2032 ድረስ የሚራዘም ሲሆን፣ የህጉ ትንታኔ እንደሚያሳየው ለሰራተኞች እና ለኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ክፍያን ጨምሮ በዓመት 2.7 ሚሊዮን ዶላር በጀት ይጠይቃል።
ኤማ ሰኞ ዕለት በካፒቶል በሰጠችው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ እንዳብራራችው፣ FTDን በነርቭ መጎዳት በሽታዎች መዝገብ ውስጥ ማካተት የካሊፎርኒያ ታካሚዎችን መቁጠር ብቻ ሳይሆን፣ በካሊፎርኒያ የሚገኙ የባዮቴክ ተመራማሪዎች ህክምና እና ፈውስ ለማግኘት የሚፈልጉትን ጠቃሚ የመረጃ ቋት መገንባት ነው። ባለቤቷ ለመጀመሪያ ጊዜ በ2022 በበሽታው መያዙ እንደታወቀ የጠቀሰችው ኤማ፣ አሁን ላይ ህመሙን የሚያዘገይ ወይም የሚያቆም ህክምና እንደሌለ ብታምንም፣ የህመሙን መረጃዎች መሰብሰብ ግን ለምርምር ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳለው ተናግራለች። ታዋቂው ተዋናይ ስለሚገኝበት ሁኔታ ተጠይቃ ስትመልስም፣ በዚህ እጅግ ጨካኝ በሆነ በሽታ ውስጥ ሆኖ ማድረግ የሚችለውን ያህል በጥሩ ሁኔታ ላይ ይገኛል ብዬ አስባለሁ ስትል ገልጻለች።
'ፒክስ ዲዚዝ' በመባልም የሚታወቀው ይህ ህመም፣ ከግንባር ጀርባ ወይም ከጆሮ አካባቢ ባሉ የጭንቅላት ክፍሎች ላይ በሚከሰት የነርቭ ሴሎች መጎዳት የሚመጣ የጭንቅላት እክል ነው። የበሽታው ምልክቶች የባህሪ እና የስብዕና ለውጥን፣ ስሜት አልባ መሆንን ፣ ውሳኔ የመስጠት፣ የመንቀሳቀስ እና የመናገር ችግርን፣ እንዲሁም ቃላትን የመረዳት አቅም ማጣትን ያካትታሉ።
የኤፍ ቲ ዲ ማህበር የጥብቅና እና የበጎ ፈቃደኞች ተሳትፎ ዳይሬክተር የሆኑት ሜጋን ቡዝቢ እንደገለጹት፣ የታካሚ ቤተሰቦች እነዚህ ምልክቶች ሲታዩ ከሐኪሞች ግልጽ የሆነ ምላሽ ለማግኘት ብዙ ጊዜ ይቸገራሉ። ዳይሬክተሯ አክለውም፣ ይህ ሁኔታ ለብዙ የካሊፎርኒያ ቤተሰቦች የFTD ምርመራ ውጤትን ለማግኘት የሚያደርጉት ረጅም እና አድካሚ ጉዞ እውነታ መሆኑን አብራርተዋል። በአሁኑ ወቅት በሽታውን ለማከም የሚረዱ ህክምናዎች እጅግ ውስን ሲሆኑ፣ ፈውስም እስካሁን አልተገኘለትም።
3 days ago
በአረንጓዴ ዐሻራ ወደ ዓለም አቀፍ እውቅና የተሻገረችው ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 27፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ዘላቂ የኢኮኖሚ ዕድገትን ለማረጋገጥ እና የአየር ንብረት ለውጥን ለመቀልበስ ያለመው ሀገራዊ የአረንጓዴ ዐሻራ ንቅናቄ፤ ዛሬ በአንድ ጀንበር ከ800 ሚሊየን በላይ ችግኞችን የመትከል ታሪካዊ መርሃ ግብሩን በስኬት እያከናወነ ይገኛል።
የዘንድሮውን ሀገራዊ የችግኝ ተከላ እና የደረሰበትን ምዕራፍ አስመልክቶ የብሔራዊ አረንጓዴ አሻራ ቴክኒክ ኮሚቴ አስተባባሪ አደፍርስ ወርቁ (ዶ/ር) በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ፤ አረንጓዴ አሻራ በሀገር ውስጥ ካመጣው ሥነ-ምህዳራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ለውጥ ባሻገር ትልቅ የዲፕሎማሲ ድል እያስገኘ ነው ብለዋል፡፡
ከስምንት ዓመታት በፊት በከፍተኛ ሁኔታ የሙቀት መጨመር፣ የደን ሽፋን መመናመን፣ የዱር እንስሳት ስደት እና የግብርና ምርታማነት መቀነስ የመሳሰሉ ችግሮች እየጨመሩ መጥተው ነበር፡፡ ይህን አሳሳቢ ሁኔታ ለመቀልበስ የተጀመረው አረንጓዴ ዐሻራ፤ እስካሁን ባለው ሂደት ከ48 ቢሊየን በላይ ችግኞችን መትከል መቻሉን ዶ/ር አደፍርስ ገልጸዋል።
ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ጀምሮ ሁሉም ዜጋ እና ተቋማት በአንድነት በተሳተፉበት በዚህ ንቅናቄ፤ አሳሳቢ የነበረው የኢትዮጵያ የደን ሽፋን 23.6 መድረስ ችሏል።
ኢትዮጵያ ባከናወነችው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር ከዚህ ቀደም በየዓመቱ እስከ 92 ሺህ ሄክታር ይደርስ የነበረው የደን ጭፍጨፋ አሁን ላይ ወደ 27 ሺህ ሄክታር ዝቅ እንዲል ማድረግ ተችሏል።
በመርሃ ግብሩም የደን፣ የፍራፍሬ፣ የእንስሳት መኖ እና ልዩ ልዩ ችግኞችን በማፍላት እና በመንከባከብ ሂደት ከ2 ነጥብ 4 ሚሊየን በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የስራ ዕድል ተፈጥሯል።
ይህም ለዜጎች የገቢ ምንጭ ከመሆኑም በላይ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ እና ምርት እና ምርታማነትን ለመጨመር አስችሏል።
በአረንጓዴ ዐሻራ የመጣው ድምር ሥነ-ምህዳራዊ ውጤት፤ እንደ ሐረማያ እና አቢጃታ-ሻላ ያሉ የደረቁ እና መጠናቸው በከፍኛ ሁኔታ የቀነሱ ሐይቆች ዳግም እንዲያንሰራሩ ጭምር ትልቅ ሚና መጫወቱን ዶክተር አደፍርስ ወርቁ አብራርተዋል።
እንደ ዶ/ር አደፍርስ ማብራሪያ፣ የአረንጓዴ አሻራ ንቅናቄ ሲጀመር በተለይም በዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ዘንድ ከፍተኛ ጥርጣሬ ነበረ።
ነገር ግን ኢትዮጵያ ከእቅዷ በላይ በመትከል እና አጽድቃ በማሳየት ይህንን ትርክት መቀየር ችላለች ብለዋል።
አሁን ላይ ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ስለ አየር ንብረት ለውጥ በንድፈ ሀሳብ ከመወያየት ባለፈ፤ የኢትዮጵያን ተግባራዊ ስራዎች እና ውጤቶች በማየት ከኢትዮጵያ ጋር መስራት ጀምሯል።
ይሄም ሀገሪቱ በዲፕሎማሲው መስክ ትልቅ ትሩፋት እንድታገኝ እና ስሟ በበጎ እንዲነሳ ማድረጉ አስተባባሪው ጠቅሰዋል።
ኢትዮጵያ 32ኛውን የተባበሩት መንግስታት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ (COP 32) እንድታዘጋጅ መመረጧ የዚሁ ጥረት ውጤት መሆኑንና፤ ጉባኤውም ትክክለኛው የአፍሪካ ኮፕ እንደሚሆን ዶክተር አደፍርስ አብራርተዋል።
አረንጓዴ ዐሻራ አርሶ አደሩን እና አርብቶ አደሩን ከሚያጋጥመው የድርቅ ፈተና ከመታደግ ባለፈ፣ ኢትዮጵያ የዓለምን የአየር ንብረት ለውጥ ጉዳትን በመቀልበስ ረገድ ግንባር ቀደም ተዋናይ መሆኗን በተግባር ያረጋገጠ ነው።
በዓለምሰገድ አሳዬ
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 27፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ዘላቂ የኢኮኖሚ ዕድገትን ለማረጋገጥ እና የአየር ንብረት ለውጥን ለመቀልበስ ያለመው ሀገራዊ የአረንጓዴ ዐሻራ ንቅናቄ፤ ዛሬ በአንድ ጀንበር ከ800 ሚሊየን በላይ ችግኞችን የመትከል ታሪካዊ መርሃ ግብሩን በስኬት እያከናወነ ይገኛል።
የዘንድሮውን ሀገራዊ የችግኝ ተከላ እና የደረሰበትን ምዕራፍ አስመልክቶ የብሔራዊ አረንጓዴ አሻራ ቴክኒክ ኮሚቴ አስተባባሪ አደፍርስ ወርቁ (ዶ/ር) በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ፤ አረንጓዴ አሻራ በሀገር ውስጥ ካመጣው ሥነ-ምህዳራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ለውጥ ባሻገር ትልቅ የዲፕሎማሲ ድል እያስገኘ ነው ብለዋል፡፡
ከስምንት ዓመታት በፊት በከፍተኛ ሁኔታ የሙቀት መጨመር፣ የደን ሽፋን መመናመን፣ የዱር እንስሳት ስደት እና የግብርና ምርታማነት መቀነስ የመሳሰሉ ችግሮች እየጨመሩ መጥተው ነበር፡፡ ይህን አሳሳቢ ሁኔታ ለመቀልበስ የተጀመረው አረንጓዴ ዐሻራ፤ እስካሁን ባለው ሂደት ከ48 ቢሊየን በላይ ችግኞችን መትከል መቻሉን ዶ/ር አደፍርስ ገልጸዋል።
ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ጀምሮ ሁሉም ዜጋ እና ተቋማት በአንድነት በተሳተፉበት በዚህ ንቅናቄ፤ አሳሳቢ የነበረው የኢትዮጵያ የደን ሽፋን 23.6 መድረስ ችሏል።
ኢትዮጵያ ባከናወነችው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር ከዚህ ቀደም በየዓመቱ እስከ 92 ሺህ ሄክታር ይደርስ የነበረው የደን ጭፍጨፋ አሁን ላይ ወደ 27 ሺህ ሄክታር ዝቅ እንዲል ማድረግ ተችሏል።
በመርሃ ግብሩም የደን፣ የፍራፍሬ፣ የእንስሳት መኖ እና ልዩ ልዩ ችግኞችን በማፍላት እና በመንከባከብ ሂደት ከ2 ነጥብ 4 ሚሊየን በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የስራ ዕድል ተፈጥሯል።
ይህም ለዜጎች የገቢ ምንጭ ከመሆኑም በላይ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ እና ምርት እና ምርታማነትን ለመጨመር አስችሏል።
በአረንጓዴ ዐሻራ የመጣው ድምር ሥነ-ምህዳራዊ ውጤት፤ እንደ ሐረማያ እና አቢጃታ-ሻላ ያሉ የደረቁ እና መጠናቸው በከፍኛ ሁኔታ የቀነሱ ሐይቆች ዳግም እንዲያንሰራሩ ጭምር ትልቅ ሚና መጫወቱን ዶክተር አደፍርስ ወርቁ አብራርተዋል።
እንደ ዶ/ር አደፍርስ ማብራሪያ፣ የአረንጓዴ አሻራ ንቅናቄ ሲጀመር በተለይም በዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ዘንድ ከፍተኛ ጥርጣሬ ነበረ።
ነገር ግን ኢትዮጵያ ከእቅዷ በላይ በመትከል እና አጽድቃ በማሳየት ይህንን ትርክት መቀየር ችላለች ብለዋል።
አሁን ላይ ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ስለ አየር ንብረት ለውጥ በንድፈ ሀሳብ ከመወያየት ባለፈ፤ የኢትዮጵያን ተግባራዊ ስራዎች እና ውጤቶች በማየት ከኢትዮጵያ ጋር መስራት ጀምሯል።
ይሄም ሀገሪቱ በዲፕሎማሲው መስክ ትልቅ ትሩፋት እንድታገኝ እና ስሟ በበጎ እንዲነሳ ማድረጉ አስተባባሪው ጠቅሰዋል።
ኢትዮጵያ 32ኛውን የተባበሩት መንግስታት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ (COP 32) እንድታዘጋጅ መመረጧ የዚሁ ጥረት ውጤት መሆኑንና፤ ጉባኤውም ትክክለኛው የአፍሪካ ኮፕ እንደሚሆን ዶክተር አደፍርስ አብራርተዋል።
አረንጓዴ ዐሻራ አርሶ አደሩን እና አርብቶ አደሩን ከሚያጋጥመው የድርቅ ፈተና ከመታደግ ባለፈ፣ ኢትዮጵያ የዓለምን የአየር ንብረት ለውጥ ጉዳትን በመቀልበስ ረገድ ግንባር ቀደም ተዋናይ መሆኗን በተግባር ያረጋገጠ ነው።
በዓለምሰገድ አሳዬ
4 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) ግብፅ የቀይ ባህር ዘብን ለመቀላቀል ገና እንዳልወሰነች አስታወቀች፡፡ በሳኡዲ አረቢያ አስተባባሪነት ባለፈው ሳምንት በተደረገ አንድ ስብሰባ ቀይ ባህርንና ባብኤል መንደብን ለመጠበቅ በሚል አንድ ጥምር ሀይል መመስረቱ ይፋ መሆኑ ይታወሳል፡፡ በዚህ ጥምር ሀይል ውስጥ 14 አገራት ለመሳተፍ ፈቃደኝነታቸውን መግለፃቸው የሚጠቅስ መግለጫም ወጥቶ ነበር፡፡ ከእነዚህ አገራት ውስጥ ግብፅ እንዳለችበት በስፋት ተዘግቧል፡፡
ይሁን እንጂ የግብፅ መንግስታዊው አህራም ጋዜጣ በዛሬ ዘገባው አገሪቱ ጥምረቱ ውስጥ ለመግባት ገና ውሳኔ ላይ እንዳልደረሰች ገልጿል፡፡ አንድ ከፍተኛ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ባለስልጣንን በምንጭነት የጠቀሰው ዘገባው ‹‹ውሳኔ ላይ ለመድረስ አስፈላጊውን ሂደቶች ለማለፍ የሚያስችሉ ህጋዊና ህገመንግስታዊ ጉዳዮች እየተመረመሩ ነው›› ብሏል፡፡
ምንጩ እንደገለፁት ማንኛውም የግብፅ ተሳትፎ በተወካዮች ምክር ቤት ይሁንታን የሚፈልግ ሲሆን ከአገሪቱ ህገ መንግስትና ህጎች ጋር መጣጣም ይኖርበታል፡፡ የአገሪቱን ብሄራዊ ጥቅም መጠበቅና ተገቢ የሆኑ ተቋማዊ መስፈርቶችን ማሟላት እንደሚገባውም አስረድተዋል፡፡
በቀይ ባህር ዘብ ጥምር ሀይል ውስጥ የተካተቱ አገራት በጋራ ያወጡት መግለጫ ላይ ግብፅ ስሟ መስፈሩ በጥምር ሀይሉ ውስጥ ለመሳተፍ የመጨረሻ ውሳኔ ላይ ደርሳለች ማለት እንዳልሆነም አብራርተዋል፡፡
ይሁን እንጂ የግብፅ መንግስታዊው አህራም ጋዜጣ በዛሬ ዘገባው አገሪቱ ጥምረቱ ውስጥ ለመግባት ገና ውሳኔ ላይ እንዳልደረሰች ገልጿል፡፡ አንድ ከፍተኛ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ባለስልጣንን በምንጭነት የጠቀሰው ዘገባው ‹‹ውሳኔ ላይ ለመድረስ አስፈላጊውን ሂደቶች ለማለፍ የሚያስችሉ ህጋዊና ህገመንግስታዊ ጉዳዮች እየተመረመሩ ነው›› ብሏል፡፡
ምንጩ እንደገለፁት ማንኛውም የግብፅ ተሳትፎ በተወካዮች ምክር ቤት ይሁንታን የሚፈልግ ሲሆን ከአገሪቱ ህገ መንግስትና ህጎች ጋር መጣጣም ይኖርበታል፡፡ የአገሪቱን ብሄራዊ ጥቅም መጠበቅና ተገቢ የሆኑ ተቋማዊ መስፈርቶችን ማሟላት እንደሚገባውም አስረድተዋል፡፡
በቀይ ባህር ዘብ ጥምር ሀይል ውስጥ የተካተቱ አገራት በጋራ ያወጡት መግለጫ ላይ ግብፅ ስሟ መስፈሩ በጥምር ሀይሉ ውስጥ ለመሳተፍ የመጨረሻ ውሳኔ ላይ ደርሳለች ማለት እንዳልሆነም አብራርተዋል፡፡
4 days ago
ይከፈላል ተብሏል‼️
በምርጫ ቦርድ እና በምርጫ አስፈጻሚዎች መካከል ያለው የክፍያ ውዝግብ።
በሰባተኛው አገራዊ ምርጫ የተሳተፉ የመስክ አሠልጣኞች፣ የማስተባበሪያ ኃላፊዎችና የቆጠራ አስተባባሪዎች በገቡት ውል መሠረት ሊከፈላቸው የሚገባው የአገልግሎትና የጉዞ አበል ክፍያ እንዳልተፈጸመላቸው ገለጹ።
ባለሙያዎቹ ኃላፊነታቸውን በሰዓቱና በውሉ መሠረት ቢያጠናቅቁም ክፍያው በመዘገየቱ ከፍተኛ የኢኮኖሚና የሥነ ልቦና ጫና እንደደረሰባቸው በመግለጽ የቦርዱን ኃላፊዎች ለጥያቄያቸው ግዴለሽነት አሳይተዋል ሲሉ ከሰዋል።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በበኩሉ ለሪፖርተር ጋዜጣ በሰጠው ምላሽ፣ ክፍያው ከመፈጸሙ በፊት አሠልጣኞቹ በውላቸው መሠረት ሥራቸውን በአግባቡ መወጣታቸውን የማጣራትና የማረጋገጥ ሥራ መሠራት እንዳለበት አስታውቋል።
ቦርዱ አክሎም ምርጫው የተካሄደው የበጀት ዓመቱ መዝጊያ ላይ በመሆኑ የነበረው በጀት በማለቁ ተጨማሪ በጀት እንዲለቀቅለት መጠየቁንና በጀቱ ሲፈቀድ ማጣራቱ ተጠናቆ ክፍያው እንደሚፈጸም አብራርቷል።
Seledadotio
Seledadotio
በምርጫ ቦርድ እና በምርጫ አስፈጻሚዎች መካከል ያለው የክፍያ ውዝግብ።
በሰባተኛው አገራዊ ምርጫ የተሳተፉ የመስክ አሠልጣኞች፣ የማስተባበሪያ ኃላፊዎችና የቆጠራ አስተባባሪዎች በገቡት ውል መሠረት ሊከፈላቸው የሚገባው የአገልግሎትና የጉዞ አበል ክፍያ እንዳልተፈጸመላቸው ገለጹ።
ባለሙያዎቹ ኃላፊነታቸውን በሰዓቱና በውሉ መሠረት ቢያጠናቅቁም ክፍያው በመዘገየቱ ከፍተኛ የኢኮኖሚና የሥነ ልቦና ጫና እንደደረሰባቸው በመግለጽ የቦርዱን ኃላፊዎች ለጥያቄያቸው ግዴለሽነት አሳይተዋል ሲሉ ከሰዋል።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በበኩሉ ለሪፖርተር ጋዜጣ በሰጠው ምላሽ፣ ክፍያው ከመፈጸሙ በፊት አሠልጣኞቹ በውላቸው መሠረት ሥራቸውን በአግባቡ መወጣታቸውን የማጣራትና የማረጋገጥ ሥራ መሠራት እንዳለበት አስታውቋል።
ቦርዱ አክሎም ምርጫው የተካሄደው የበጀት ዓመቱ መዝጊያ ላይ በመሆኑ የነበረው በጀት በማለቁ ተጨማሪ በጀት እንዲለቀቅለት መጠየቁንና በጀቱ ሲፈቀድ ማጣራቱ ተጠናቆ ክፍያው እንደሚፈጸም አብራርቷል።
Seledadotio
Seledadotio
Sponsored by
Surafel
4 days ago
የሴዶ እና የጆኒ ታላቅ የMMA ፍልሚያ ነሐሴ 21 ይካሄዳል!
#fastmereja :-በኢትዮጵያ የማርሻል አርትስ እና የቦክስ ስፖርት ታሪክ ያልተነካውን እምቅ አቅም ለዓለም ለማሳየትና ስፖርቱን ለወጣቶች የቋሚ ገቢ ምንጭ ለማድረግ ያለመው ''አድዋ ፋይት ናይት 2" (ETFC 002) ታላቅ የውድድር ምሽት ነሀሴ 21 እንደሚካሄድ በዛሬዉ እለት ተገለፀ።
ነሀሴ 21 በሚካሄደው በዚህ ውድድር ላይ በስፖርት አፍቃሪያን ዘንድ ከፍተኛ ትኩረትን የሳበው እና በጉጉት የሚጠበቀው ዋና ፍልሚያ (Main Event) በጆኒ (Johnny) እና በሴዶ (Sedo) መካከል የሚደረገው ድብልቅ ማርሻል አርት (MMA) ግጥሚያ እንደሆነ ተገልጿል።
ዛሬ በተሰጠው የጋዜጣዊ መግለጫ ወቅት ተወዳዳሪዎች በፊት ለፊት ፍጥጫ (Face-to face) የተገናኙ ሲሆን እርስ በእርስ ያቀረቧቸው የተፎካካሪነት እና የስነ-ልቦና የበላይነት የመውሰጃ አስተያየቶች በስፍራው የነበረውን ስሜት ያጋገሉት ሲሆን፣ ሁለቱም ስፖርተኞች ለነሐሴ 21ዱ ታላቅ ፍልሚያ ያላቸውን ከፍተኛ ዝግጁነትና የማሸነፍ በራስ መተማመን አሳይተዋል።
የውድድሩ አዘጋጅና የስዊት ቦክስ መስራች እና ስራ አ አቶ ጌታቸው መለሰ በበኩላቸው፣ ETFC 002 የቀደመው ETFC 001 ከተካሄደበት ፍጥነትና ሁኔታ በተሻለ መልኩ በከፍተኛ ደረጃ ተዘጋጅቶ የቀረበ መሆኑን ገልጸዋል።
አዘጋጆቹ ለፕሮግራሙ መዘገየት ይቅርታ በመጠየቅ፣በተወዳዳሪዎቹ የስነ-ምግባር ጥንካሬ ላይ ሙሉ እምነት እንዳላቸውና ስፖርተኞቹ ሀገራቸውን በዓለም አቀፍ መድረክ ማስጠራት የሚችሉ መሆናቸውን አብራርተዋል።
በምሽቱ 11 የተመረጡ ፍልሚያዎች የሚካሄዱ ሲሆን፣ 4 የቦክስ (Boxing) 4 የኤምኤምኤ (MMA) 3 የሙአይ ታይ (Muay Thai) ፍልሚያዎች ናቸው።
በዝግጅቱ ላይ የሴቶች ተሳትፎ ልዩ ቦታ የተሰጠው ሲሆን፣ አትሌት አብስላት እና ዛራ በተወዳዳሪነት የሚሳተፉ ሲሆን በቀጣዩ «አድዋ ፋይት ናይት 003» ውድድር ላይ ደግሞ የሴት ተወዳዳሪዎች ቁጥር እንዲጨምርና ሰፊ ተሳትፎ እንዲኖራቸው ትኩረት ተሰጥቶ እንደሚሰራ ተጠቅሷል።
በሌላ በኩል፣ በቀደሙት ዝግጅቶች የነበረውን የመቀመጫ መደራረብ ችግር ሙሉ በሙሉ ለመቅረፍ የተሰራ ሲሆን በዚህም ተመልካቾች ትኬት በሚቆርጡበት ወቅት ቀጥታ የመቀመጫ ቦታቸውን (Seat) መርጠው እንዲይዙ እንደሚደረግም ነዉ የተገለፀዉ።
አዘጋጆቹ እንዳብራሩት፣ በቅርቡ በሚካሄዱት ETFC-003 እና ETFC-004 የውድድር መድረኮች ላይ የሀገር ውስጥ ስፖርተኞች ከውጭ ሀገር ተወዳዳሪዎች ጋር እንዲጋጠሙ እንደሚደረግ የተገለፀ ሲሆን ይህም በሚቀጥሉት ሁለት ዓመታት ውስጥ እንደ ኡሲክ (Usyk) ያሉ ታዋቂ የዓለም አቀፍ ቦክስ ውድድሮችን በኢትዮጵያ ውስጥ ለማዘጋጀት ለተያዘው ታላቅ ዕቅድ መንገድ የሚከፍት ነው ተብሏል።
ይህ ዝግጅት በአድዋ ድል መታሰቢያ፣ በአዲስ አበባ ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ፣ የስፖርት አመራሮች እንዲሁም አጋር ድርጅቶች አስተዋጽኦ የሚካሄድ ሲሆን፣ የስፖርት አፍቃሪያን የነሐሴ 21ዱን የሴዶ እና ጆኒ ፍልሚያ በከፍተኛ ጉጉት በመጠበቅ ላይ ይገኛሉ።
📷 ከበደ መክብብ
#fastmereja :-በኢትዮጵያ የማርሻል አርትስ እና የቦክስ ስፖርት ታሪክ ያልተነካውን እምቅ አቅም ለዓለም ለማሳየትና ስፖርቱን ለወጣቶች የቋሚ ገቢ ምንጭ ለማድረግ ያለመው ''አድዋ ፋይት ናይት 2" (ETFC 002) ታላቅ የውድድር ምሽት ነሀሴ 21 እንደሚካሄድ በዛሬዉ እለት ተገለፀ።
ነሀሴ 21 በሚካሄደው በዚህ ውድድር ላይ በስፖርት አፍቃሪያን ዘንድ ከፍተኛ ትኩረትን የሳበው እና በጉጉት የሚጠበቀው ዋና ፍልሚያ (Main Event) በጆኒ (Johnny) እና በሴዶ (Sedo) መካከል የሚደረገው ድብልቅ ማርሻል አርት (MMA) ግጥሚያ እንደሆነ ተገልጿል።
ዛሬ በተሰጠው የጋዜጣዊ መግለጫ ወቅት ተወዳዳሪዎች በፊት ለፊት ፍጥጫ (Face-to face) የተገናኙ ሲሆን እርስ በእርስ ያቀረቧቸው የተፎካካሪነት እና የስነ-ልቦና የበላይነት የመውሰጃ አስተያየቶች በስፍራው የነበረውን ስሜት ያጋገሉት ሲሆን፣ ሁለቱም ስፖርተኞች ለነሐሴ 21ዱ ታላቅ ፍልሚያ ያላቸውን ከፍተኛ ዝግጁነትና የማሸነፍ በራስ መተማመን አሳይተዋል።
የውድድሩ አዘጋጅና የስዊት ቦክስ መስራች እና ስራ አ አቶ ጌታቸው መለሰ በበኩላቸው፣ ETFC 002 የቀደመው ETFC 001 ከተካሄደበት ፍጥነትና ሁኔታ በተሻለ መልኩ በከፍተኛ ደረጃ ተዘጋጅቶ የቀረበ መሆኑን ገልጸዋል።
አዘጋጆቹ ለፕሮግራሙ መዘገየት ይቅርታ በመጠየቅ፣በተወዳዳሪዎቹ የስነ-ምግባር ጥንካሬ ላይ ሙሉ እምነት እንዳላቸውና ስፖርተኞቹ ሀገራቸውን በዓለም አቀፍ መድረክ ማስጠራት የሚችሉ መሆናቸውን አብራርተዋል።
በምሽቱ 11 የተመረጡ ፍልሚያዎች የሚካሄዱ ሲሆን፣ 4 የቦክስ (Boxing) 4 የኤምኤምኤ (MMA) 3 የሙአይ ታይ (Muay Thai) ፍልሚያዎች ናቸው።
በዝግጅቱ ላይ የሴቶች ተሳትፎ ልዩ ቦታ የተሰጠው ሲሆን፣ አትሌት አብስላት እና ዛራ በተወዳዳሪነት የሚሳተፉ ሲሆን በቀጣዩ «አድዋ ፋይት ናይት 003» ውድድር ላይ ደግሞ የሴት ተወዳዳሪዎች ቁጥር እንዲጨምርና ሰፊ ተሳትፎ እንዲኖራቸው ትኩረት ተሰጥቶ እንደሚሰራ ተጠቅሷል።
በሌላ በኩል፣ በቀደሙት ዝግጅቶች የነበረውን የመቀመጫ መደራረብ ችግር ሙሉ በሙሉ ለመቅረፍ የተሰራ ሲሆን በዚህም ተመልካቾች ትኬት በሚቆርጡበት ወቅት ቀጥታ የመቀመጫ ቦታቸውን (Seat) መርጠው እንዲይዙ እንደሚደረግም ነዉ የተገለፀዉ።
አዘጋጆቹ እንዳብራሩት፣ በቅርቡ በሚካሄዱት ETFC-003 እና ETFC-004 የውድድር መድረኮች ላይ የሀገር ውስጥ ስፖርተኞች ከውጭ ሀገር ተወዳዳሪዎች ጋር እንዲጋጠሙ እንደሚደረግ የተገለፀ ሲሆን ይህም በሚቀጥሉት ሁለት ዓመታት ውስጥ እንደ ኡሲክ (Usyk) ያሉ ታዋቂ የዓለም አቀፍ ቦክስ ውድድሮችን በኢትዮጵያ ውስጥ ለማዘጋጀት ለተያዘው ታላቅ ዕቅድ መንገድ የሚከፍት ነው ተብሏል።
ይህ ዝግጅት በአድዋ ድል መታሰቢያ፣ በአዲስ አበባ ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ፣ የስፖርት አመራሮች እንዲሁም አጋር ድርጅቶች አስተዋጽኦ የሚካሄድ ሲሆን፣ የስፖርት አፍቃሪያን የነሐሴ 21ዱን የሴዶ እና ጆኒ ፍልሚያ በከፍተኛ ጉጉት በመጠበቅ ላይ ይገኛሉ።
📷 ከበደ መክብብ
4 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙሉ የራስ ገዝነት መብቱን ለመተግበር ባደረገው የመዋቅር ማስተካከያ ምክንያት ከ500 በላይ አስተዳደራዊ ሰራተኞች እና 50 መምህራን ያለመደብ መቅረታቸውን ኤስቢኤስ ራድዮ ከአውስትራሊያ ዘግበ። የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ዶክተር ሳሙኤል ክፍሌ ማንም ሰራተኛ እንዳልተባረረ ገልጸው፤ የተጎዱት በጡረታ፣ በካሳ ወይም በቅርቡ በሚጀመረው የንግድ እንቅስቃሴ እንደሚካተቱ ተናግረዋል።
ፎርቹን ጋዜጣ እንደዘገበው ደግሞ ምደባው ለአስተዳደር ሰራተኞች በፈተና፣ ለመምህራን ደግሞ በትምህርት ዝግጅት አግባብነት ላይ ተመስርቶ እየተከናወነ ነው። በሀገሪቱ ከሚገኙ 46 የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች መካከል የመጀመሪያው ሞዴል የሆነው የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሪፎርም እርምጃ፣ ቀጣይ ተመሳሳይ እርምጃ ለመውሰድ ለሚዘጋጁት እንደ ጅማ፣ ባህር ዳር፣ ጎንደር፣ መቀሌ እና መሰል ታላላቅ ዩኒቨርሲቲዎች ማሳያ ይሆናል ተብሏል።
ፎርቹን ጋዜጣ እንደዘገበው ደግሞ ምደባው ለአስተዳደር ሰራተኞች በፈተና፣ ለመምህራን ደግሞ በትምህርት ዝግጅት አግባብነት ላይ ተመስርቶ እየተከናወነ ነው። በሀገሪቱ ከሚገኙ 46 የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች መካከል የመጀመሪያው ሞዴል የሆነው የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሪፎርም እርምጃ፣ ቀጣይ ተመሳሳይ እርምጃ ለመውሰድ ለሚዘጋጁት እንደ ጅማ፣ ባህር ዳር፣ ጎንደር፣ መቀሌ እና መሰል ታላላቅ ዩኒቨርሲቲዎች ማሳያ ይሆናል ተብሏል።
5 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) ‹‹የሱዳንና የኤርትራ አጋርነት ለአፍሪካ ቀንድና ቀይ ባህር መረጋጋት ከፍተኛ ሚና ይጫወታል፡፡›› ሲሉ በኤርትራ የሱዳን አምባሳደር ገለፁ፡፡ በኤርትራ የሱዳን አምባሳደር የሆኑት ኦሳማ አህመድ አደል ባሪ ዛሬ ባሰራጩት ዘለግ ያለ ፅሁፍ የሁለቱን አገራት ግንኙነት ጠቀሜታ አጉልተው ለማሳየት ጥረዋል፡፡ በሱዳን ሆራይዘን ጋዜጣ ላይ በሰፈረው በዚህ ፅሁፋቸው ‹‹ቀይ ባህርና የአፍሪካ ቀንድ በአሁኑ ጊዜ በፍጥነት በሚለዋወጥ ጂኦፖለቲካዊ ባህርይና በመርከቦች ጉዞ፣ በአቅርቦት ሰንሰለት፣ በነዳጅ ሀብትና በተፈጥሮ ሀብት ላይ በሚደረግ ፉክክር ወሳኝ ምእራፍ ውስጥ ይገኛሉ›› በማለት ጀምረዋል፡፡
አስከትለውም ከዚህ በመነሳት ከክልላዊ አጋርነት በተሻለ ሰፋ ያሉ የደህንነት፣ የልማትና ዘላቂ መረጋጋትን አላማው ያደረገ ስትራቴጂያዊ ጥምረት እንደሚያስፈልግ አስረድተዋል፡፡ አምባሳደሩ ሲቀጥሉም ‹‹ከዚህ አንፃር የሱዳንና ኤርትራ ስትራቴጂያዊ አጋርነት የተረጋጋ ቀጣናዊ የሀይል ሚዛን እንዲኖር የሚያስችል ትልቅ መሰረት ነው›› ያሉ ሲሆን ሁለቱ አገራት በቀይ ባህርና በአፍሪካ ቀንድ ዙሪያ የጋራ ፍላጎት እንዳላቸው ገልፀዋል፡፡ ጨምረውም ‹‹ሱዳን በቀይ ባህር ዳርቻዋ በኩል ሰሜን አፍሪካን ከምስራቅና ከመካከለኛው አፍሪካ ጋር የምታገናኝ ድልድይ ናት፡፡
እንዲሁም ባላት የግብርና፣ የውሀና የማእድን ሀብቶች በቀጠናው ውስጥ ትልቅ የልማት ሞተር ሆና ማገልገል ትችላለች፡፡ በሌላ በኩል ኤርትራ ደግሞ በቀይ ባህር ላይ ልዩ የሆነ ጂኦግራፊያዊ አቀማመጥ ያላት ከመሆኑም በላይ ሰፊ የባህር ዳርቻና ተስፋ ሰጪ ወደቦችን የያዘች ናት፡፡ ስለዚህም እነዚህ ጉዳዮች ኢኮኖሚያዊ ውህደት ለመፍጠርና በቀጠናው ውስጥ የተረጋጋ ፖለቲካ ለመፍጠር ምሰሶ ሆነው ሊያገለግሉ ይችላሉ›› በማለት ገልፀው ሁለቱ አገራት ዘላቂነት ያለውና ረጅም ራእይ የሰነቀ ስትራቴጂያዊ አጋርነት መፍጠራቸውን አስረድተዋል፡፡
አስከትለውም ከዚህ በመነሳት ከክልላዊ አጋርነት በተሻለ ሰፋ ያሉ የደህንነት፣ የልማትና ዘላቂ መረጋጋትን አላማው ያደረገ ስትራቴጂያዊ ጥምረት እንደሚያስፈልግ አስረድተዋል፡፡ አምባሳደሩ ሲቀጥሉም ‹‹ከዚህ አንፃር የሱዳንና ኤርትራ ስትራቴጂያዊ አጋርነት የተረጋጋ ቀጣናዊ የሀይል ሚዛን እንዲኖር የሚያስችል ትልቅ መሰረት ነው›› ያሉ ሲሆን ሁለቱ አገራት በቀይ ባህርና በአፍሪካ ቀንድ ዙሪያ የጋራ ፍላጎት እንዳላቸው ገልፀዋል፡፡ ጨምረውም ‹‹ሱዳን በቀይ ባህር ዳርቻዋ በኩል ሰሜን አፍሪካን ከምስራቅና ከመካከለኛው አፍሪካ ጋር የምታገናኝ ድልድይ ናት፡፡
እንዲሁም ባላት የግብርና፣ የውሀና የማእድን ሀብቶች በቀጠናው ውስጥ ትልቅ የልማት ሞተር ሆና ማገልገል ትችላለች፡፡ በሌላ በኩል ኤርትራ ደግሞ በቀይ ባህር ላይ ልዩ የሆነ ጂኦግራፊያዊ አቀማመጥ ያላት ከመሆኑም በላይ ሰፊ የባህር ዳርቻና ተስፋ ሰጪ ወደቦችን የያዘች ናት፡፡ ስለዚህም እነዚህ ጉዳዮች ኢኮኖሚያዊ ውህደት ለመፍጠርና በቀጠናው ውስጥ የተረጋጋ ፖለቲካ ለመፍጠር ምሰሶ ሆነው ሊያገለግሉ ይችላሉ›› በማለት ገልፀው ሁለቱ አገራት ዘላቂነት ያለውና ረጅም ራእይ የሰነቀ ስትራቴጂያዊ አጋርነት መፍጠራቸውን አስረድተዋል፡፡
7 days ago
ሲ.አይ.ኤ እና ሞሳድ የኢራን አዲሱን የበላይ መሪ ሙጅተባ ኻመነኢን ለማግኘት የሚያደርጉት ጥረት ትኩረት ስቧል
#ዓለም | የብሪታንያው The Times ጋዜጣ የደህንነት ምንጮችን ጠቅሶ እንደዘገበው፣ የአሜሪካው ሲ.አይ.ኤ (CIA) እና የእስራኤሉ ሞሳድ (Mossad) የኢራን አዲሱ የበላይ መሪ ሙጅተባ ኻመነኢ የት እንዳሉ ለማረጋገጥ እና ሁኔታቸውን ለመከታተል የስለላ ጥረታቸውን አጠናክረዋል።
ሪፖርቱ እንደሚለው፣ ሙጅተባ ኻመነኢ ከአባታቸው ሞት በኋላ የኢራንን ከፍተኛ አመራር ቢረከቡም፣ በአደባባይ አልታዩም፤ ስልክ፣ ኮምፒውተር ወይም ሌሎች የኤሌክትሮኒክስ መገናኛ ዘዴዎችን እንደማይጠቀሙም ይገለጻል። በዚህ ምክንያት በሳተላይት እና በሳይበር መንገድ የሚደረገው ክትትል ውጤታማ እንዳልሆነ ተነግሯል።
በዚህ ሁኔታ የምዕራባውያን የደህንነት ተቋማት ትኩረታቸውን ከኤሌክትሮኒክስ ስለላ ወደ Human Intelligence (HUMINT) ወይም በሰዎች በኩል የሚሰበሰብ መረጃ ላይ ማዞራቸው ተዘግቧል። አንዳንድ የቀድሞ የሞሳድ ባለስልጣናት እንደሚሉት፣ ሙጅተባ መልእክቶችን በብዙ ደረጃ በተደራጁ ተላላኪዎች እንደሚያስተላልፉ ይገመታል።
ሆኖም እስካሁን ድረስ ሙጅተባ ኻመነኢ የት እንዳሉ፣ በምን ዓይነት የጤና ሁኔታ እንዳሉ ወይም በቀጥታ አገሪቱን እየመሩ መሆናቸው በገለልተኛ ምንጮች አልተረጋገጠም። የአሜሪካና የእስራኤል ባለሥልጣናትም እነዚህን ሪፖርቶች በይፋ አላረጋገጡም።
አንዳንድ ሚዲያዎች ሙጅተባ ኻመነኢ በሕይወት ስለመኖራቸው ወይም ስለ ምትክ ሰዎች (body doubles) የሚያነሱት ጥርጣሬ መኖሩን ቢዘግቡም፣ እነዚህ አባባሎች በገለልተኛ ማስረጃ ያልተረጋገጡ ግምቶች መሆናቸውን የዓለም አቀፍ የዜና ተቋማት ያስገነዝባሉ።
ተንታኞች እንደሚሉት፣ ሙጅተባ ኻመነኢ በሕዝብ ፊት አለመታየታቸው በኢራን የሥልጣን አወቃቀር፣ በአብዮታዊ ዘብ (IRGC) ያለው ተጽዕኖ እና በቀጣናው የደህንነት ሁኔታ ላይ የተለያዩ ጥያቄዎችን እያስነሳ ነው። ነገር ግን ከስለላ ሪፖርቶች ባሻገር የተረጋገጠ ኦፊሴላዊ መረጃ አሁንም አልቀረበም።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#ዓለም | የብሪታንያው The Times ጋዜጣ የደህንነት ምንጮችን ጠቅሶ እንደዘገበው፣ የአሜሪካው ሲ.አይ.ኤ (CIA) እና የእስራኤሉ ሞሳድ (Mossad) የኢራን አዲሱ የበላይ መሪ ሙጅተባ ኻመነኢ የት እንዳሉ ለማረጋገጥ እና ሁኔታቸውን ለመከታተል የስለላ ጥረታቸውን አጠናክረዋል።
ሪፖርቱ እንደሚለው፣ ሙጅተባ ኻመነኢ ከአባታቸው ሞት በኋላ የኢራንን ከፍተኛ አመራር ቢረከቡም፣ በአደባባይ አልታዩም፤ ስልክ፣ ኮምፒውተር ወይም ሌሎች የኤሌክትሮኒክስ መገናኛ ዘዴዎችን እንደማይጠቀሙም ይገለጻል። በዚህ ምክንያት በሳተላይት እና በሳይበር መንገድ የሚደረገው ክትትል ውጤታማ እንዳልሆነ ተነግሯል።
በዚህ ሁኔታ የምዕራባውያን የደህንነት ተቋማት ትኩረታቸውን ከኤሌክትሮኒክስ ስለላ ወደ Human Intelligence (HUMINT) ወይም በሰዎች በኩል የሚሰበሰብ መረጃ ላይ ማዞራቸው ተዘግቧል። አንዳንድ የቀድሞ የሞሳድ ባለስልጣናት እንደሚሉት፣ ሙጅተባ መልእክቶችን በብዙ ደረጃ በተደራጁ ተላላኪዎች እንደሚያስተላልፉ ይገመታል።
ሆኖም እስካሁን ድረስ ሙጅተባ ኻመነኢ የት እንዳሉ፣ በምን ዓይነት የጤና ሁኔታ እንዳሉ ወይም በቀጥታ አገሪቱን እየመሩ መሆናቸው በገለልተኛ ምንጮች አልተረጋገጠም። የአሜሪካና የእስራኤል ባለሥልጣናትም እነዚህን ሪፖርቶች በይፋ አላረጋገጡም።
አንዳንድ ሚዲያዎች ሙጅተባ ኻመነኢ በሕይወት ስለመኖራቸው ወይም ስለ ምትክ ሰዎች (body doubles) የሚያነሱት ጥርጣሬ መኖሩን ቢዘግቡም፣ እነዚህ አባባሎች በገለልተኛ ማስረጃ ያልተረጋገጡ ግምቶች መሆናቸውን የዓለም አቀፍ የዜና ተቋማት ያስገነዝባሉ።
ተንታኞች እንደሚሉት፣ ሙጅተባ ኻመነኢ በሕዝብ ፊት አለመታየታቸው በኢራን የሥልጣን አወቃቀር፣ በአብዮታዊ ዘብ (IRGC) ያለው ተጽዕኖ እና በቀጣናው የደህንነት ሁኔታ ላይ የተለያዩ ጥያቄዎችን እያስነሳ ነው። ነገር ግን ከስለላ ሪፖርቶች ባሻገር የተረጋገጠ ኦፊሴላዊ መረጃ አሁንም አልቀረበም።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
Sponsored by
Surafel
7 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) ክርስቲያኖ ሮናልዶ የሰርግ ፕሮግራም መራዘሙ ተገለፀ፡፡ ክርስቲያኖ ሮናልዶና ጆርጂያና ሮዲሪጌዝ አሁን በስፔን ማሎርካ የእረፍት ጊዜያቸውን እያሳለፉ ይገኛሉ፡፡ ጥንዶቹ ቀለበት ማሰራቸውን ካስታወቁ ከአንድ አመት በኋላ አሁን የሰርጋቸው ወሬ የናኘው ሁለቱም የዳይመንድ ቀለበት አስረው በመታየታቸው ብቻ አይደለም፡፡ አንድ የፖርቹጋል ቴሌቪዥን ጣቢያ ለሰርጉ የጥሪ ካርድ መበተኑን የሚገልፅ መረጃ በማሰራጨቱም ጭምር ነው፡፡
እንደመረጃው የጥንዶቹ የሰርግ ፕሮግራም ነገ ኦገስት 1 ቀን በፖርቹጋል የሚከናወን ይሆናል፡፡ ቪ ፕላስ ፋማ የተሰኘው የቴሌቪዥን ፕሮግራም የሰርጉን የጥሪ ካርድ እንደተመለከተ ገልፆ ሰርጉ ኦገስት 1 ቀን በ5 ሰአት በፖርቹጋል ሲንትራ ከተማ በሚገኘው ኩኒታ ደ ሬግሌሪያ ውስጥ እንደሚካሄድ ገልፆም ነበር፡፡ ይህንን ተከትሎ ሰሞኑን በማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ የዚህ ሰርግ ጉዳይ በስፋት ተሰራጭቷል፡፡ ይሁን እንጂ ሆላ የተሰኘው የፖርቹጋል ጋዜጣ ዛሬ ባቀረበው ዘገባ ቢያንስ በዚህ ሳምንት መጨረሻ የሰርግ ፕሮግራሙ እንደማይካሄድ ማረጋገጡን አስታውቋል፡፡
ምክንያቱም ታሪካዊው ኩኒታ ደ ሬግሌሪያ ቪላ ቅዳሜና እሁድ ለቱሪስቶች ክፍት ነው፡፡ የሰርግ ፕሮግራሙ የሚካሄድ ቢሆን ቪላው ዝግ እንደሚሆንና ትኬትም መሸጥ ይቆም እንደነበር አስረድቷል፡፡ ክሪስቲያኖ ሮናልዶና ሮድሪጌዝ ጥንድ ከሆኑ 10 አመት አልፏቸዋል፡፡ በዚህ ግንኙነታቸውም 5 ልጆችን ለማፍራት የቻሉ ሲሆን ቀለበት ያሰረላት የዛሬ አመት ገደማ ነበር፡፡ ሁለቱም ጥንዶች ሰርግ የማድረግ ፍላጎት እንዳላቸው በአደባባይ በተደጋጋሚ ጊዜ ተናግረዋል፡፡
ሮናልዶ በአንድ ወቅት በሰጠው ቃለ ምልልስ ‹‹እሷን በሰርግ የማገባት አሁን ትክክለኛው ጊዜ በመሆኑ ነው፡፡ ይህንን ስል የልጆቼ እናት በመሆኗ ሳይሆን በአለም ላይ እጅግ የማፈቅራት ሴት ስለሆነች ነው›› ብሎ ነበር፡፡ ሰሞኑን የሰርጉ ወሬ በስፋት ቢሰራጭም ይህ ቢያንስ ነገ እንደማይሆን ተረጋግጧል፡፡ እንደሆላ ጋዜጣ ዘገባ ሰርጉ በቅርብ ጊዜያት ውስጥ የመሆንም እድል የለውም፡፡
እንደመረጃው የጥንዶቹ የሰርግ ፕሮግራም ነገ ኦገስት 1 ቀን በፖርቹጋል የሚከናወን ይሆናል፡፡ ቪ ፕላስ ፋማ የተሰኘው የቴሌቪዥን ፕሮግራም የሰርጉን የጥሪ ካርድ እንደተመለከተ ገልፆ ሰርጉ ኦገስት 1 ቀን በ5 ሰአት በፖርቹጋል ሲንትራ ከተማ በሚገኘው ኩኒታ ደ ሬግሌሪያ ውስጥ እንደሚካሄድ ገልፆም ነበር፡፡ ይህንን ተከትሎ ሰሞኑን በማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ የዚህ ሰርግ ጉዳይ በስፋት ተሰራጭቷል፡፡ ይሁን እንጂ ሆላ የተሰኘው የፖርቹጋል ጋዜጣ ዛሬ ባቀረበው ዘገባ ቢያንስ በዚህ ሳምንት መጨረሻ የሰርግ ፕሮግራሙ እንደማይካሄድ ማረጋገጡን አስታውቋል፡፡
ምክንያቱም ታሪካዊው ኩኒታ ደ ሬግሌሪያ ቪላ ቅዳሜና እሁድ ለቱሪስቶች ክፍት ነው፡፡ የሰርግ ፕሮግራሙ የሚካሄድ ቢሆን ቪላው ዝግ እንደሚሆንና ትኬትም መሸጥ ይቆም እንደነበር አስረድቷል፡፡ ክሪስቲያኖ ሮናልዶና ሮድሪጌዝ ጥንድ ከሆኑ 10 አመት አልፏቸዋል፡፡ በዚህ ግንኙነታቸውም 5 ልጆችን ለማፍራት የቻሉ ሲሆን ቀለበት ያሰረላት የዛሬ አመት ገደማ ነበር፡፡ ሁለቱም ጥንዶች ሰርግ የማድረግ ፍላጎት እንዳላቸው በአደባባይ በተደጋጋሚ ጊዜ ተናግረዋል፡፡
ሮናልዶ በአንድ ወቅት በሰጠው ቃለ ምልልስ ‹‹እሷን በሰርግ የማገባት አሁን ትክክለኛው ጊዜ በመሆኑ ነው፡፡ ይህንን ስል የልጆቼ እናት በመሆኗ ሳይሆን በአለም ላይ እጅግ የማፈቅራት ሴት ስለሆነች ነው›› ብሎ ነበር፡፡ ሰሞኑን የሰርጉ ወሬ በስፋት ቢሰራጭም ይህ ቢያንስ ነገ እንደማይሆን ተረጋግጧል፡፡ እንደሆላ ጋዜጣ ዘገባ ሰርጉ በቅርብ ጊዜያት ውስጥ የመሆንም እድል የለውም፡፡
8 days ago
“አደይ አዲስ ዓመት ታላቅ የንግድ ኤክስፖ እና ፌስቲቫል” ይፋ ሆነ
#fastmereja I የ2019 አዲስ ዓመት ምክንያት በማድረግ በአዲስ ኮንቬንሽን ሴንተር ሊካሄድ የታቀደው “አደይ አዲስ ዓመት ታላቅ የንግድ ኤክስፖ እና ፌስቲቫል” ይፋ ተደርጓል። ኤክስፖው ከነሐሴ 21 ቀን 2018 ዓ.ም እስከ ጳጉሜን 05 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ለ15 ቀናት እንደሚቆይ አዘጋጆቹ አስታውቀዋል።
ይህ ታላቅ የንግድ እና የፌስቲቫል መድረክ በማስተር ፒስ ትሬዲንግ እና ራይት ኤቨንትስ ትብብር የተዘጋጀ ሲሆን፣ አዘጋጆቹ ለሚዲያ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ እንዳመለከቱት ዝግጅቱ ለስሚት እና ለአካባቢው ነዋሪዎች የገበያ አማራጮችን በቅርበት የሚያቀርብ ነው። በኤክስፖው ላይ ከ200 በላይ የሀገር ውስጥ አምራቾች፣ አስመጪዎች፣ የዕደ-ጥበብ ባለሙያዎች እና የአገልግሎት ሰጪ ተቋማት ምርትና አገልግሎታቸውን በተፎካካሪ እና በተመጣጣኝ ዋጋ እንደሚያቀርቡ ተገልጿል።
ከንግድ እንቅስቃሴው ጎን ለጎን ፌስቲቫሉ በየቀኑ 15 አርቲስቶች የሚሳተፉበት የቀጥታ የሙዚቃ ኮንሰርት፣ የፋሽን ሾው፣ የህፃናት መጫወቻዎች እና የበጎ አድራጎት ስራዎችን ያካተተ እንደሚሆን ተጠቅሷል። በተጨማሪም የኪነ-ጥበብ መድረኮችን ጨምሮ የመጽሐፍት አውደ ርዕይ እና ሽያጭ ይካሄዳል።
በ15 ቀናቱ የፌስቲቫል ቆይታ ከ80,000 በላይ ጎብኚዎች እና ደንበኞች ይገበያያሉ ተብሎ የሚጠበቅ ሲሆን፣ አዘጋጆቹ ቅድመ ዝግጅታቸውን አጠናቀው የኤግዚቢሽን ቦታዎችን በመሸጥ ላይ እንደሚገኙ አስታውቀዋል።
#ኹነት
#fastmereja I የ2019 አዲስ ዓመት ምክንያት በማድረግ በአዲስ ኮንቬንሽን ሴንተር ሊካሄድ የታቀደው “አደይ አዲስ ዓመት ታላቅ የንግድ ኤክስፖ እና ፌስቲቫል” ይፋ ተደርጓል። ኤክስፖው ከነሐሴ 21 ቀን 2018 ዓ.ም እስከ ጳጉሜን 05 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ለ15 ቀናት እንደሚቆይ አዘጋጆቹ አስታውቀዋል።
ይህ ታላቅ የንግድ እና የፌስቲቫል መድረክ በማስተር ፒስ ትሬዲንግ እና ራይት ኤቨንትስ ትብብር የተዘጋጀ ሲሆን፣ አዘጋጆቹ ለሚዲያ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ እንዳመለከቱት ዝግጅቱ ለስሚት እና ለአካባቢው ነዋሪዎች የገበያ አማራጮችን በቅርበት የሚያቀርብ ነው። በኤክስፖው ላይ ከ200 በላይ የሀገር ውስጥ አምራቾች፣ አስመጪዎች፣ የዕደ-ጥበብ ባለሙያዎች እና የአገልግሎት ሰጪ ተቋማት ምርትና አገልግሎታቸውን በተፎካካሪ እና በተመጣጣኝ ዋጋ እንደሚያቀርቡ ተገልጿል።
ከንግድ እንቅስቃሴው ጎን ለጎን ፌስቲቫሉ በየቀኑ 15 አርቲስቶች የሚሳተፉበት የቀጥታ የሙዚቃ ኮንሰርት፣ የፋሽን ሾው፣ የህፃናት መጫወቻዎች እና የበጎ አድራጎት ስራዎችን ያካተተ እንደሚሆን ተጠቅሷል። በተጨማሪም የኪነ-ጥበብ መድረኮችን ጨምሮ የመጽሐፍት አውደ ርዕይ እና ሽያጭ ይካሄዳል።
በ15 ቀናቱ የፌስቲቫል ቆይታ ከ80,000 በላይ ጎብኚዎች እና ደንበኞች ይገበያያሉ ተብሎ የሚጠበቅ ሲሆን፣ አዘጋጆቹ ቅድመ ዝግጅታቸውን አጠናቀው የኤግዚቢሽን ቦታዎችን በመሸጥ ላይ እንደሚገኙ አስታውቀዋል።
#ኹነት
9 days ago
የኢትዮጵያ አየር መንገድ 1.4 ትሪልየን ብር ገቢ ማግኘቱን አስታወቀ
**
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዛሬ ሐምሌ 22 ቀን 2018 ዓ.ም በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ፤ በበጀት ዓመቱ 1.4 ትሪልየን ብር ገቢ ማግኘቱን አስታውቋል።
የአየር መንገዱ ዋና ስራ አስፈፃሚ መስፍን ጣሰው እንደገለፁት፤ በአመቱ ከ20.1 ሚልየን በላይ መንገደኞችን እና 297 ሺህ ቶን የካርጎ ጭነቶችን ማጓጓዝ ተችሏል።
ከዚህ በተጨማሪም አየር መንገዱ የተለያዩ የአውሮፕላን ክፍሎችን የሚያመርት ሲሆን በዘንድሮው በጀት አመትም ለ68 አውሮፕላኖች የሚበቃ መለዋወጫ በማምረት ለቦይንግ ማቅረቡን ገልፀዋል።
በዚህም 6.2 ሚልየን ዶላር ገቢ ማግኘት እንደቻለ አስታውቀዋል።
Seledadotio
Seledadotio
**
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዛሬ ሐምሌ 22 ቀን 2018 ዓ.ም በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ፤ በበጀት ዓመቱ 1.4 ትሪልየን ብር ገቢ ማግኘቱን አስታውቋል።
የአየር መንገዱ ዋና ስራ አስፈፃሚ መስፍን ጣሰው እንደገለፁት፤ በአመቱ ከ20.1 ሚልየን በላይ መንገደኞችን እና 297 ሺህ ቶን የካርጎ ጭነቶችን ማጓጓዝ ተችሏል።
ከዚህ በተጨማሪም አየር መንገዱ የተለያዩ የአውሮፕላን ክፍሎችን የሚያመርት ሲሆን በዘንድሮው በጀት አመትም ለ68 አውሮፕላኖች የሚበቃ መለዋወጫ በማምረት ለቦይንግ ማቅረቡን ገልፀዋል።
በዚህም 6.2 ሚልየን ዶላር ገቢ ማግኘት እንደቻለ አስታውቀዋል።
Seledadotio
Seledadotio
10 days ago
ዘንድሮ ከ9 ሺህ በላይ ፍቺዎች ተመዝግበዋል
#ethiopia | የሲቪል ምዝገባና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ በ2018 በጀት ዓመት መጨረሻ 9,558 የፍቺ ምዝገባዎች መከናወናቸውን አስታወቀ።
ይህንን ዛሬ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ የኤጀንሲው ዋና ዳይሬክተር አቶ ዮሴፍ ንጉሤ ገልጸዋል።
በሪፖርቱ መሠረት፣ በበጀት ዓመቱ በአምስቱ የኩነት ምዝገባ ዓይነቶች (ልደት፣ ሞት፣ ጋብቻ፣ ፍቺ እና ጉዲፈቻ) በድምሩ 500,363 ምዝገባዎች ተከናውነዋል።
በተመሳሳይ 37,149 የጋብቻ ምዝገባዎችም ተመዝግበዋል።
ኤጀንሲው በዓመቱ ከ1.5 ሚሊዮን በላይ ተገልጋዮችን በማስተናገድ 2.4 ሚሊዮን የሚጠጉ አገልግሎቶችን እንደሰጠ ገልጿል።
እንዲሁም በጤና ተቋማትና በፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤቶች 11 ቅርንጫፎች የአንድ መስኮት አገልግሎት በመክፈት የልደት፣ የሞት እና ሌሎች የሲቪል ምዝገባ አገልግሎቶችን ተደራሽ ማድረጉን አስታውቋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#ethiopia #addisababa #civilregistration #marriage #divorce #news
#ethiopia | የሲቪል ምዝገባና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ በ2018 በጀት ዓመት መጨረሻ 9,558 የፍቺ ምዝገባዎች መከናወናቸውን አስታወቀ።
ይህንን ዛሬ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ የኤጀንሲው ዋና ዳይሬክተር አቶ ዮሴፍ ንጉሤ ገልጸዋል።
በሪፖርቱ መሠረት፣ በበጀት ዓመቱ በአምስቱ የኩነት ምዝገባ ዓይነቶች (ልደት፣ ሞት፣ ጋብቻ፣ ፍቺ እና ጉዲፈቻ) በድምሩ 500,363 ምዝገባዎች ተከናውነዋል።
በተመሳሳይ 37,149 የጋብቻ ምዝገባዎችም ተመዝግበዋል።
ኤጀንሲው በዓመቱ ከ1.5 ሚሊዮን በላይ ተገልጋዮችን በማስተናገድ 2.4 ሚሊዮን የሚጠጉ አገልግሎቶችን እንደሰጠ ገልጿል።
እንዲሁም በጤና ተቋማትና በፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤቶች 11 ቅርንጫፎች የአንድ መስኮት አገልግሎት በመክፈት የልደት፣ የሞት እና ሌሎች የሲቪል ምዝገባ አገልግሎቶችን ተደራሽ ማድረጉን አስታውቋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#ethiopia #addisababa #civilregistration #marriage #divorce #news
Sponsored by
Surafel
10 days ago
በ2018 በጀት ዓመት ከ9ሺህ በላይ ፍቺ መመዝገቡን ኤጀንሲው አስታወቀ
የሲቪል ምዝገባ እና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ ሰኔ 30 በተጠናቀቀው የ2018 በጀት ዓመት 9 ሺህ 558 ፍቺ መመዝገቡን አስታውቋል፡፡
ኤጀንሲው ይህንን የገለፀው የበጀት ዓመቱን አፈጻጸም አስመልክቶ ዛሬ ሐምሌ 21 ቀን 2018 ዓ.ም. ለመገናኛ ብዙኃን በሰጠው ጋዜጣዊ መግልጫ ነው፡፡
በመግለጫው ወቅት የኤጀንሲው ዋና ዳይሬክተር አቶ ዮሴፍ ንጉሤ እንደገለፁት በበጀት ዓመቱ በአምስቱ የኩነት የምዝገባ ዓይነቶች ማለትም፡- ልደት፣ ሞት፣ ፍቺ፣ ጋብቻ፣ ጉዲፈቻ 500 ሺህ 363 ምዝገባዎች መከናወናቸውን ተናግረዋል።
በ2018 ዓ.ም. እስከ ሰኔ 30 ድረስ 37ሺህ 149 የጋብቻ ምዝገባ ተከናውኗል ተብሏል፡፡
1 ሚሊዮን 500 ሺህ ተገልጋዮች በኤጀንሲው በኩል አገልግሎት ማግኘታቸውን ጠቅሰው፤ 2 ሚሊዮን 400 ሺህ አገልግሎቶች እንደተሰጡ አብራርተዋል።
ኤጀንሲው ይህን አገልግሎት ሲሰጥ በአንድ ቦታ ብቻ ሳይሆን ሳይሆን በጤና ተቋማት እና በሌሎችም ተቋማት በመንቀሳቀስ ጭምር እንደሆነ አስረድተዋል።
በተለይ ከተማዋ ላይ በሚገኙ የጤና ተቋማት ላይ የአንድ መስኮት የአገልግሎት መስጫ በመክፈት የልደት እና የሞት ምዝገባ እያከናወነ መሆኑን አብራርተዋል።
ከዚህ በተጨማሪ የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ላይም የአንድ መስኮት አገልግሎት መስጫ በመክፈት በ11 የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ላይ አገልግሎት እየሰጠ እንደሚገኝ ጠቁመዋል።
በተመስገን ተጋፋው
የሲቪል ምዝገባ እና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ ሰኔ 30 በተጠናቀቀው የ2018 በጀት ዓመት 9 ሺህ 558 ፍቺ መመዝገቡን አስታውቋል፡፡
ኤጀንሲው ይህንን የገለፀው የበጀት ዓመቱን አፈጻጸም አስመልክቶ ዛሬ ሐምሌ 21 ቀን 2018 ዓ.ም. ለመገናኛ ብዙኃን በሰጠው ጋዜጣዊ መግልጫ ነው፡፡
በመግለጫው ወቅት የኤጀንሲው ዋና ዳይሬክተር አቶ ዮሴፍ ንጉሤ እንደገለፁት በበጀት ዓመቱ በአምስቱ የኩነት የምዝገባ ዓይነቶች ማለትም፡- ልደት፣ ሞት፣ ፍቺ፣ ጋብቻ፣ ጉዲፈቻ 500 ሺህ 363 ምዝገባዎች መከናወናቸውን ተናግረዋል።
በ2018 ዓ.ም. እስከ ሰኔ 30 ድረስ 37ሺህ 149 የጋብቻ ምዝገባ ተከናውኗል ተብሏል፡፡
1 ሚሊዮን 500 ሺህ ተገልጋዮች በኤጀንሲው በኩል አገልግሎት ማግኘታቸውን ጠቅሰው፤ 2 ሚሊዮን 400 ሺህ አገልግሎቶች እንደተሰጡ አብራርተዋል።
ኤጀንሲው ይህን አገልግሎት ሲሰጥ በአንድ ቦታ ብቻ ሳይሆን ሳይሆን በጤና ተቋማት እና በሌሎችም ተቋማት በመንቀሳቀስ ጭምር እንደሆነ አስረድተዋል።
በተለይ ከተማዋ ላይ በሚገኙ የጤና ተቋማት ላይ የአንድ መስኮት የአገልግሎት መስጫ በመክፈት የልደት እና የሞት ምዝገባ እያከናወነ መሆኑን አብራርተዋል።
ከዚህ በተጨማሪ የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ላይም የአንድ መስኮት አገልግሎት መስጫ በመክፈት በ11 የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ላይ አገልግሎት እየሰጠ እንደሚገኝ ጠቁመዋል።
በተመስገን ተጋፋው
12 days ago
8ኛው ግራንድ አፍሪካን ረን፡ የታዋቂ አትሌቶች ተሳታፊነት እና የ2026 ቶዮታ ኮሮላ ሽልማትን ይዞ ሊካሄድ ነው
የዲያስፖራ ማህበረሰብን የሚያሰባስበው ዓመታዊው የ5 ኪሎ ሜትር ሩጫ ዝግጅቱን አጠናቀቀ
በዋሽንግተን ዲሲ፣ ሜሪላንድ እና ቨርጂኒያ አካባቢ የሚካሄደውና የዲያስፖራውን ማህበረሰብ ለማቀራረብ የሚዘጋጀው 8ኛው ግራንድ አፍሪካን ረን በፈረንጆቹ አቆጣጠር በመጪው ኦክቶበር 10, 2026 (ጥቅምት 1, 2019 ዓ.ም.) እንደሚካሄድ በተሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ይፋ ተደረገ።
‘አብሮነት መሻል ነው’ በሚል መሪ ቃል የሚካሄደው ይህ ዝግጅት፤ የዲያስፖራውን ማህበረሰብ ማሰባሰብ፣ በውጭ ሀገር የሚያድጉ ህፃናትና ወጣቶች ከባህላቸው ጋር እንዲቀራረቡ ማድረግ እና ለተለያዩ ማህበራዊ በጎ ስራዎች ገቢ ማሰባሰብን ዋና ዓላማው ያደረገ ነው። ለዝግጅቱ የሚሆን የምዝገባ ሂደት በአዘጋጆቹ ኦፊሴላዊ ዌብሳይት (www.africanrun.com) ላይ መጀመሩም ተገልጿል።
የዝግጅቱ ቀዳሚ አጋር የሆነው አሌክሳንድሪያ ቶዮታ ለተሳታፊዎች የሚሆን የ2026 ቶዮታ ኮሮላ መኪና በሽልማት መልክ አዘጋጅቷል። “ሁሉም አሸናፊ ነው” በሚለው የዝግጅቱ መርህ መሠረት፣ በሩጫው የተሳተፈ ማንኛውም ሰው ርቀቱን ያጠናቀቀበት ሰዓት ሳይወሰነው በቀረበው የመኪና ሽልማት ዕጣ ውስጥ እኩል የመሳተፍና የማሸነፍ ዕድል ይኖረዋል። አሸናፊውም በውድድሩ ማጠቃለያ ላይ በሚወጣ የሎተሪ ዕጣ የሚለይ ይሆናል።
በዘንድሮው 8ኛ ዙር ዝግጅት ላይ ታዋቂዎቹ አትሌቶች ረዳት ኮሚሽነር ደራርቱ ቱሉ፣ አትሌት ጥሩነሽ ዲባባ እና አትሌት ስለሺ ስህን በክብር እንግድነት ተገኝተው ተሳታፊዎችን እንደሚያበረታቱ ታውቋል። አትሌት ደራርቱ ቱሉ ለዝግጅቱ ያላትን ድጋፍ ስትገልፅ “ሀገራችንን በዓለም መድረክ ያስጠራው የአትሌቲክስ ስፖርት በውጭ ለሚገኙ ወገኖቻችን የመሰባሰቢያ መድረክ መሆኑ ዝግጅቱን ልዩ ያደረገዋል” ብላለች።
በጋዜጣዊ መግለጫው ላይ የተገኙት የአሌክሳንድሪያ ቶዮታ፣ የኢትዮ ቴሌኮም፣ የዳሽን ባንክ፣ የጊፍት ሪል እስቴት፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድ እና የሮሚንግ ሮስተር ከፍተኛ የኃላፊነት ቦታ ያላቸው ተወካዮች በበኩላቸው፤ ከተቋሞቻቸው ማህበራዊ ኃላፊነት አንጻር ከግራንድ አፍሪካን ረን ጋር ያላቸውን አጋርነት በመግለፅ ለዝግጅቱ ስኬት የሚያደርጉትን ድጋፍ አጠናክረው እንደሚቀጥሉ አረጋግጠዋል።
የውድድሩ ዋና አዘጋጅ ዶክተር ጋሻው አብዛ ዝግጅቱ ከአንድ ቀን የ5 ኪሎ ሜትር የቤተሰብ ሩጫ ባሻገር፣ የዲያስፖራውን ማህበረሰብ እርስ በእርስ በማቀራረብ ረገድ ከፍተኛ ድልድይ እየሆነ መምጣቱን ገልጸዋል።
ግራንድ አፍሪካን ረን በየዓመቱ ጥቅምት ወር በገባ በሁለተኛው ቅዳሜ የሚካሄድና ብዙሃኑን የሚያሳትፍ ዓመታዊ የጎዳና ላይ የመዝናኛ ሩጫ ሲሆን፣ ዘንድሮ ለ8ኛ ጊዜ ይካሄዳል።
ለበለጠ መረጃ እና ለምዝገባ፦
ተቋም: Nova Connections - Grand African Run
ፌስቡክ: www.facebook.com/GrandRunD...
ዌብሳይት: www.africanrun.com
የዲያስፖራ ማህበረሰብን የሚያሰባስበው ዓመታዊው የ5 ኪሎ ሜትር ሩጫ ዝግጅቱን አጠናቀቀ
በዋሽንግተን ዲሲ፣ ሜሪላንድ እና ቨርጂኒያ አካባቢ የሚካሄደውና የዲያስፖራውን ማህበረሰብ ለማቀራረብ የሚዘጋጀው 8ኛው ግራንድ አፍሪካን ረን በፈረንጆቹ አቆጣጠር በመጪው ኦክቶበር 10, 2026 (ጥቅምት 1, 2019 ዓ.ም.) እንደሚካሄድ በተሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ይፋ ተደረገ።
‘አብሮነት መሻል ነው’ በሚል መሪ ቃል የሚካሄደው ይህ ዝግጅት፤ የዲያስፖራውን ማህበረሰብ ማሰባሰብ፣ በውጭ ሀገር የሚያድጉ ህፃናትና ወጣቶች ከባህላቸው ጋር እንዲቀራረቡ ማድረግ እና ለተለያዩ ማህበራዊ በጎ ስራዎች ገቢ ማሰባሰብን ዋና ዓላማው ያደረገ ነው። ለዝግጅቱ የሚሆን የምዝገባ ሂደት በአዘጋጆቹ ኦፊሴላዊ ዌብሳይት (www.africanrun.com) ላይ መጀመሩም ተገልጿል።
የዝግጅቱ ቀዳሚ አጋር የሆነው አሌክሳንድሪያ ቶዮታ ለተሳታፊዎች የሚሆን የ2026 ቶዮታ ኮሮላ መኪና በሽልማት መልክ አዘጋጅቷል። “ሁሉም አሸናፊ ነው” በሚለው የዝግጅቱ መርህ መሠረት፣ በሩጫው የተሳተፈ ማንኛውም ሰው ርቀቱን ያጠናቀቀበት ሰዓት ሳይወሰነው በቀረበው የመኪና ሽልማት ዕጣ ውስጥ እኩል የመሳተፍና የማሸነፍ ዕድል ይኖረዋል። አሸናፊውም በውድድሩ ማጠቃለያ ላይ በሚወጣ የሎተሪ ዕጣ የሚለይ ይሆናል።
በዘንድሮው 8ኛ ዙር ዝግጅት ላይ ታዋቂዎቹ አትሌቶች ረዳት ኮሚሽነር ደራርቱ ቱሉ፣ አትሌት ጥሩነሽ ዲባባ እና አትሌት ስለሺ ስህን በክብር እንግድነት ተገኝተው ተሳታፊዎችን እንደሚያበረታቱ ታውቋል። አትሌት ደራርቱ ቱሉ ለዝግጅቱ ያላትን ድጋፍ ስትገልፅ “ሀገራችንን በዓለም መድረክ ያስጠራው የአትሌቲክስ ስፖርት በውጭ ለሚገኙ ወገኖቻችን የመሰባሰቢያ መድረክ መሆኑ ዝግጅቱን ልዩ ያደረገዋል” ብላለች።
በጋዜጣዊ መግለጫው ላይ የተገኙት የአሌክሳንድሪያ ቶዮታ፣ የኢትዮ ቴሌኮም፣ የዳሽን ባንክ፣ የጊፍት ሪል እስቴት፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድ እና የሮሚንግ ሮስተር ከፍተኛ የኃላፊነት ቦታ ያላቸው ተወካዮች በበኩላቸው፤ ከተቋሞቻቸው ማህበራዊ ኃላፊነት አንጻር ከግራንድ አፍሪካን ረን ጋር ያላቸውን አጋርነት በመግለፅ ለዝግጅቱ ስኬት የሚያደርጉትን ድጋፍ አጠናክረው እንደሚቀጥሉ አረጋግጠዋል።
የውድድሩ ዋና አዘጋጅ ዶክተር ጋሻው አብዛ ዝግጅቱ ከአንድ ቀን የ5 ኪሎ ሜትር የቤተሰብ ሩጫ ባሻገር፣ የዲያስፖራውን ማህበረሰብ እርስ በእርስ በማቀራረብ ረገድ ከፍተኛ ድልድይ እየሆነ መምጣቱን ገልጸዋል።
ግራንድ አፍሪካን ረን በየዓመቱ ጥቅምት ወር በገባ በሁለተኛው ቅዳሜ የሚካሄድና ብዙሃኑን የሚያሳትፍ ዓመታዊ የጎዳና ላይ የመዝናኛ ሩጫ ሲሆን፣ ዘንድሮ ለ8ኛ ጊዜ ይካሄዳል።
ለበለጠ መረጃ እና ለምዝገባ፦
ተቋም: Nova Connections - Grand African Run
ፌስቡክ: www.facebook.com/GrandRunD...
ዌብሳይት: www.africanrun.com
13 days ago
ዓይኖቹን ወደ ማስታወቂያ ሰሌዳነት የለወጠው ጉደኛ አትሌት
#ethiopia | በ1996ቱ የአትላንታ ኦሊምፒክ ወቅት አዘጋጆቹ የፑማ ኩባንያን የንግድ ምልክት ከስፖርት መድረኩ ለማራቅ ጥረት አድርገው ነበር።
ነገር ግን እንግሊዛዊው የሩጫ ሻምፒዮን ሊንፎርድ ክሪስቲ የኦሊምፒክ ባለስልጣናትን ያስደነገጠ ሌላ ዕቅድ ይዞ ቀረበ። የወንዶች የ100 ሜትር ውድድር ከመጀመሩ አንድ ቀን ቀደም ብሎ ክሪስቲ ጥቁር መነፅር አድርጎ የጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ተገኘ።
አትሌቱ ጥቁር መነፅሩን ሲያወልቅ በቦታው የነበሩ ጋዜጠኞችና ፎቶግራፈሮች ያልተጠበቀ ነገር ገጠማቸው።
ከዓይኖቹ ላይ ያደረጋቸው ደማቅ ሰማያዊ ኮንታክት ሌንሶች የፑማን ታዋቂ የዘላይ ድመት አርማ ይዘው ነበር። የፎቶግራፈሮች ካሜራዎች ምስሉን ወዲያውኑ የቀረፁ ሲሆን የክሪስቲ የንግድ አርማ ያረፈባቸው ዓይኖች ምስል በዓለም ዙሪያ በፍጥነት ተሰራጩት።
ምንም እንኳን የኦሊምፒክ ባለስልጣናት አትሌቱ በውድድሩ ወቅት ሌንሶቹን እንዳያደርግ በኋላ ላይ ቢከለክሉም ኩባንያው የሚፈልገውን ዓላማ አስቀድሞ አሳካ።
ክሪስቲም ቢልቦርድ፣ የቴሌቪዥን ማስታወቂያ ወይም በትራክ ልብሱ ላይ የሰፈረ አርማ ሳይያስፈልገው የራሱን ዓይኖች ወደ ማስታወቂያ ሰሌዳነት በመለወጥ በስፖርቱ ታሪክ ከታዩት ድብቅ ማስታወቂያ ስልቶች አንዱን ፈጽሟል።
በያፌት ገ/ህይወት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#ethiopia | በ1996ቱ የአትላንታ ኦሊምፒክ ወቅት አዘጋጆቹ የፑማ ኩባንያን የንግድ ምልክት ከስፖርት መድረኩ ለማራቅ ጥረት አድርገው ነበር።
ነገር ግን እንግሊዛዊው የሩጫ ሻምፒዮን ሊንፎርድ ክሪስቲ የኦሊምፒክ ባለስልጣናትን ያስደነገጠ ሌላ ዕቅድ ይዞ ቀረበ። የወንዶች የ100 ሜትር ውድድር ከመጀመሩ አንድ ቀን ቀደም ብሎ ክሪስቲ ጥቁር መነፅር አድርጎ የጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ተገኘ።
አትሌቱ ጥቁር መነፅሩን ሲያወልቅ በቦታው የነበሩ ጋዜጠኞችና ፎቶግራፈሮች ያልተጠበቀ ነገር ገጠማቸው።
ከዓይኖቹ ላይ ያደረጋቸው ደማቅ ሰማያዊ ኮንታክት ሌንሶች የፑማን ታዋቂ የዘላይ ድመት አርማ ይዘው ነበር። የፎቶግራፈሮች ካሜራዎች ምስሉን ወዲያውኑ የቀረፁ ሲሆን የክሪስቲ የንግድ አርማ ያረፈባቸው ዓይኖች ምስል በዓለም ዙሪያ በፍጥነት ተሰራጩት።
ምንም እንኳን የኦሊምፒክ ባለስልጣናት አትሌቱ በውድድሩ ወቅት ሌንሶቹን እንዳያደርግ በኋላ ላይ ቢከለክሉም ኩባንያው የሚፈልገውን ዓላማ አስቀድሞ አሳካ።
ክሪስቲም ቢልቦርድ፣ የቴሌቪዥን ማስታወቂያ ወይም በትራክ ልብሱ ላይ የሰፈረ አርማ ሳይያስፈልገው የራሱን ዓይኖች ወደ ማስታወቂያ ሰሌዳነት በመለወጥ በስፖርቱ ታሪክ ከታዩት ድብቅ ማስታወቂያ ስልቶች አንዱን ፈጽሟል።
በያፌት ገ/ህይወት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
14 days ago
(ዘ-ሐበሻ ስፖርት) የማንቸስተር ሲቲው አሰልጣኝ ኤንዞ ማሬስካ፣ የዓለም ዋንጫው ኮከብ እና የወርቅ ኳስ አሸናፊው ሮድሪ በቀጣዩ ሳምንት የወገብ ቀዶ ሕክምና እንደሚያደርግ ያረጋገጡ ሲሆን፣ ተጫዋቹ በኢቲሃድ ስታዲየም እንደሚቆይ ያላቸውን እምነት ገልጸዋል።
ሮድሪ ስፔይን በሰሜን አሜሪካ በተካሄደው የዓለም ዋንጫ ፍጻሜ አርጀንቲናን 1-0 በማሸነፍ ለሁለተኛ ጊዜ የዓለም ሻምፒዮን ስትሆን የቡድኑ አጋፋሪ እና የውድድሩ ኮከብ ተጫዋች ሆኖ መመረጡ ይታወሳል። በውድድሩ ወቅት 756 ስኬታማ ኳሶችን በማመቻቸት እና በርካታ ኳሶችን በመቀማት የቡድኑን የተከላካይ ክፍል በግንባር ቀደምትነት መርቷል።
የዓለም ዋንጫን፣ የአውሮፓ ሻምፒዮንነትን፣ አራት የፕሪሚየር ሊግ ዋንጫዎችን፣ የቻምፒዮንስ ሊግን፣ የባሎንዶርን እና ሌሎች በርካታ ዋንጫዎችን በስሙ ያጻፈው አማካይ፣ ኮንትራቱ ለመጠናቀቅ የመጨረሻ ዓመቱ ላይ በመድረሱ ወደ ማድሪድ በመመለስ ሪል ማድሪድን ሊቀላቀል ይችላል የሚሉ ዘገባዎች ሲወጡ ቆይተዋል።
ሆኖም አሰልጣኝ ኤንዞ ማሬስካ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ፣ ሮድሪ ማንኛውም አሰልጣኝ ሊያሰለጥነው የሚመኘው ድንቅ ተጫዋች መሆኑን ገልጸው፣ የዝውውር ጭ ወሬዎች በታላላቅ ተጫዋቾች ዙሪያ የተለመዱ በመሆናቸው ስጋት እንደሌላቸው ተናግረዋል።
አሰልጣኙ አክለውም ሮድሪ ሰኞ ዕለት ቀላል የወገብ ቀዶ ሕክምና እንደሚያደርግና ከቀዶ ሕክምናው በኋላ አስፈላጊውን ዕረፍት አድርጎ ወደ ቡድኑ እንደሚመለስ አስታውቀዋል። በዚህም ምክንያት ኦገስት 16 ከአርሰናል ጋር በሚደረገው የኮሚዩኒቲ ሺልድ ጨዋታ እና በፕሪሚየር ሊጉ የመክፈቻ ጨዋታ ከቦርንመስ ጋር በሚደረገው ፍልሚያ ላይ የመሰለፉ ነገር አጠራጣሪ ሆኗል።
ሮድሪ ስፔይን በሰሜን አሜሪካ በተካሄደው የዓለም ዋንጫ ፍጻሜ አርጀንቲናን 1-0 በማሸነፍ ለሁለተኛ ጊዜ የዓለም ሻምፒዮን ስትሆን የቡድኑ አጋፋሪ እና የውድድሩ ኮከብ ተጫዋች ሆኖ መመረጡ ይታወሳል። በውድድሩ ወቅት 756 ስኬታማ ኳሶችን በማመቻቸት እና በርካታ ኳሶችን በመቀማት የቡድኑን የተከላካይ ክፍል በግንባር ቀደምትነት መርቷል።
የዓለም ዋንጫን፣ የአውሮፓ ሻምፒዮንነትን፣ አራት የፕሪሚየር ሊግ ዋንጫዎችን፣ የቻምፒዮንስ ሊግን፣ የባሎንዶርን እና ሌሎች በርካታ ዋንጫዎችን በስሙ ያጻፈው አማካይ፣ ኮንትራቱ ለመጠናቀቅ የመጨረሻ ዓመቱ ላይ በመድረሱ ወደ ማድሪድ በመመለስ ሪል ማድሪድን ሊቀላቀል ይችላል የሚሉ ዘገባዎች ሲወጡ ቆይተዋል።
ሆኖም አሰልጣኝ ኤንዞ ማሬስካ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ፣ ሮድሪ ማንኛውም አሰልጣኝ ሊያሰለጥነው የሚመኘው ድንቅ ተጫዋች መሆኑን ገልጸው፣ የዝውውር ጭ ወሬዎች በታላላቅ ተጫዋቾች ዙሪያ የተለመዱ በመሆናቸው ስጋት እንደሌላቸው ተናግረዋል።
አሰልጣኙ አክለውም ሮድሪ ሰኞ ዕለት ቀላል የወገብ ቀዶ ሕክምና እንደሚያደርግና ከቀዶ ሕክምናው በኋላ አስፈላጊውን ዕረፍት አድርጎ ወደ ቡድኑ እንደሚመለስ አስታውቀዋል። በዚህም ምክንያት ኦገስት 16 ከአርሰናል ጋር በሚደረገው የኮሚዩኒቲ ሺልድ ጨዋታ እና በፕሪሚየር ሊጉ የመክፈቻ ጨዋታ ከቦርንመስ ጋር በሚደረገው ፍልሚያ ላይ የመሰለፉ ነገር አጠራጣሪ ሆኗል።
14 days ago
«የጥላቻ ንግግር ፍጻሜ፦ ዛሬ በስሜት የተነገረ ቃል ነገ ዘብጥያ ያወርዳል!»
ከአስቴር በዳኔ ንግግር በመነሳት የተዘጋጀ
በቅርቡ አርቲስት አስቴር በዳኔ የተወሰኑ ማህበረሰቦችን በጅምላ በመፈረጅ እና በዜጎች ላይ የሚደርሰውን ጥቃት «የበቀል እርምጃ» አስመስላ በማቅረብ የተናገረችው ንግግር በማህበራዊ ሚዲያ ከፍተኛ ቅሬታን አስነስቷል።
ብዙዎች የሚናገሩት አደገኛ ቃል በጊዜ ሂደት የታሪክ እና የሕግ ተጠያቂነት ያስከትላል ወይንስ እንዲሁ አየር ላይ በኖ ይቀራል በሚል ሲጠይቁ ይደመጣል።
የዓለም አቀፍ የፍትሕ ታሪክ የሚያሳየን ግን የጥላቻ ንግግሮች የትም ያህል ጊዜ ቢወስዱ የሕግ ተጠያቂነት ማስከተላቸው እንደማይቀር ነው ዛሬ በችኮላ ወይም በስሜት የሚነገሩ የሚያጋጩ ቃላት ነገ ፍትሕ በሚነግስበት ጊዜ ዘብጥያ የሚያወርዱ የሕግ ማስረጃዎች ሆነው ይመዘገባሉ።
የጥላቻ ንግግር በተለይም ታዋቂ ሰዎች ወይም የህዝብ ልሳኖች የሚያሰራጩት ሲሆን በሰላማዊ ዜጎች ላይ ለሚደርስ የጅምላ ጥቃት ማበራቻ እንደሚሆን በታሪክ በተደጋጋሚ ታይቷል።
የዓለም አቀፍ ፍርድ ቤቶችም ይህንን በግልጽ እንደ ወንጀል ፈርጀው እርምጃ ወስደዋል። እ.ኤ.አ በ1994 በሩዋንዳ ከተከሰተው አሰቃቂ የጅምላ ጨፍጨፋ በኋላ የሩዋንዳ ዓለም አቀፍ ወንጀል ትሪቡናል (ICTR) በታዋቂው የ«Media Trial» ውሳኔው መሳሪያ አንስተው የተዋጉትን ብቻ ሳይሆን በሬዲዮ እና በጋዜጣ የጥላቻ ንግግር እና የጥቃት ጥሪ ያቀረቡ የህዝብ ተሰሚነት ያላቸውን ሰዎች ለፍርድ አቅርቧል።
በዚሁ መዝገብ የRTLM ሬዲዮ ጣቢያ መስራች የነበረው ፈርዲናንድ ናሂማና እና ጋዜጠኛ ሀሰን ንጌዜ በቀጥታ ሰውን ባይገድሉም በቃላቶቻቸው ጥላቻን በመዝራታቸው እና ጥቃትን በማበራታታቸው በዓለም አቀፍ ፍርድ ቤት የጽኑ እስራት ፍርድ ተፈርዶባቸዋል።
ከዚህ በተጨማሪም ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ በተካሄደው የኑረምበርግ ፍርድ ቤት (Nuremberg Trials)፣ «ደስ ስቱርመር» በተባለው ጋዜጣ የናዚን የጥላቻ ፕሮፓጋንዳ ያሰራጭ የነበረው ጁሊየስ ሺራይቸር፣ በቀጥታ የጦር መሳሪያ ባያነሳም በቃላቱ ባሰራጨው አደገኛ ጥላቻ ምክንያት በሰው ልጅ ላይ ወንጀል በመፈጸሙ ለፍርድ ውሏል።
በተመሳሳይ ሁኔታ ከዩጎዝላቪያ መፍረስ በኋላ በተቋቋመው ዓለም አቀፍ ፍርድ ቤት (ICTY) የፖለቲከኞች እና የብዙኃን መገናኛ ሰዎች አጋጫኝ ንግግሮች በሰብዓዊነት ላይ የተፈጸሙ ወንጀሎች ተደርገው ተወስደው ለዓመታት ተከታትለው ለፍትሕ እንዲቀርቡ ተደርገዋል።
አርቲስት አስቴር በዳኔ «አማራ እና ኦርቶዶክስ የሀገር ባለቤት ነኝ ብሎ ተቀምጧል፤ ቶለሬት የማያደርግ ትውልድ ተነስቶ እየተበቀላቸው ነው» ስትል ያደረገችው ንግግር በሰላማዊ ዜጎች ላይ የሚደርስን ጥቃት እንደ «በቀል» አድርጎ በማቅረብ ወንጀልን የማበረታታት ይዘት ያለው በመሆኑ በዲጂታል ዘመን ማናቸውም የማህበራዊ ሚዲያ ንግግሮች እና መረጃዎች በቀላሉ የማይጠፉ የታሪክ ሰነዶች ናቸው።
ፍትሕ እና የሕግ የበላይነት ሙሉ በሙሉ በሚሰፍንበት ጊዜ እነዚህ ንግግሮች ማህበረሰብን ለጥቃት አጋልጠዋል በሚል በሕግ ፊት የመጠየቂያ ማስረጃዎች መሆናቸው አይቀሬ ነው።
ከሁሉም በላይ ደግሞ ማንኛውም ዜጋ ወይም ማህበረሰብ «የሀገሬ ባለቤት ነኝ» ብሎ ማሰቡና መናገሩ ህገ-መንግስታዊ እና ዜጋዊ መብቱ እንጂ በፍጹም ወንጀል ሊሆን አይችልም።
ይህንን ዜጋዊ መብት እንደ «የበላይነት ጥያቄ» አድርጎ በመተርጎም፣ በሰላማዊ ሰዎች ላይ የሚደርሰውን ግፍና ጥቃት እንደ «ተገቢ የበቀል እርምጃ» አድርጎ ማቅረብ ግን ነገ ምንይዞ እንደሚመጣ ታሪክ ይፈርዳል
በቃላት የሚዘራ ጥላቻ በሰዎች ህይወት ላይ ጥፋት ያመጣል ዛሬ በስሜት ወይም በኃይል አሰላለፍ ተሸፍነው የሚያልፉ ይመስሉ እንጂ በሕግ እና በፍትሕ ስርዓት ውስጥ የጥላቻ ንግግሮች ጊዜ አይሽራቸውም።
አርቲስቶች እና ታዋቂ ሰዎች የሚናገሩት እያንዳንዱ ቃል ነገ በፍርድ ቤት እና በታሪክ ፊት እንደሚያስጠይቅ ተረድተው ከህዝብ አጋጫኝ ንግግሮች ሊቆጠቡ ይገባል።
ከአስቴር በዳኔ ንግግር በመነሳት የተዘጋጀ
በቅርቡ አርቲስት አስቴር በዳኔ የተወሰኑ ማህበረሰቦችን በጅምላ በመፈረጅ እና በዜጎች ላይ የሚደርሰውን ጥቃት «የበቀል እርምጃ» አስመስላ በማቅረብ የተናገረችው ንግግር በማህበራዊ ሚዲያ ከፍተኛ ቅሬታን አስነስቷል።
ብዙዎች የሚናገሩት አደገኛ ቃል በጊዜ ሂደት የታሪክ እና የሕግ ተጠያቂነት ያስከትላል ወይንስ እንዲሁ አየር ላይ በኖ ይቀራል በሚል ሲጠይቁ ይደመጣል።
የዓለም አቀፍ የፍትሕ ታሪክ የሚያሳየን ግን የጥላቻ ንግግሮች የትም ያህል ጊዜ ቢወስዱ የሕግ ተጠያቂነት ማስከተላቸው እንደማይቀር ነው ዛሬ በችኮላ ወይም በስሜት የሚነገሩ የሚያጋጩ ቃላት ነገ ፍትሕ በሚነግስበት ጊዜ ዘብጥያ የሚያወርዱ የሕግ ማስረጃዎች ሆነው ይመዘገባሉ።
የጥላቻ ንግግር በተለይም ታዋቂ ሰዎች ወይም የህዝብ ልሳኖች የሚያሰራጩት ሲሆን በሰላማዊ ዜጎች ላይ ለሚደርስ የጅምላ ጥቃት ማበራቻ እንደሚሆን በታሪክ በተደጋጋሚ ታይቷል።
የዓለም አቀፍ ፍርድ ቤቶችም ይህንን በግልጽ እንደ ወንጀል ፈርጀው እርምጃ ወስደዋል። እ.ኤ.አ በ1994 በሩዋንዳ ከተከሰተው አሰቃቂ የጅምላ ጨፍጨፋ በኋላ የሩዋንዳ ዓለም አቀፍ ወንጀል ትሪቡናል (ICTR) በታዋቂው የ«Media Trial» ውሳኔው መሳሪያ አንስተው የተዋጉትን ብቻ ሳይሆን በሬዲዮ እና በጋዜጣ የጥላቻ ንግግር እና የጥቃት ጥሪ ያቀረቡ የህዝብ ተሰሚነት ያላቸውን ሰዎች ለፍርድ አቅርቧል።
በዚሁ መዝገብ የRTLM ሬዲዮ ጣቢያ መስራች የነበረው ፈርዲናንድ ናሂማና እና ጋዜጠኛ ሀሰን ንጌዜ በቀጥታ ሰውን ባይገድሉም በቃላቶቻቸው ጥላቻን በመዝራታቸው እና ጥቃትን በማበራታታቸው በዓለም አቀፍ ፍርድ ቤት የጽኑ እስራት ፍርድ ተፈርዶባቸዋል።
ከዚህ በተጨማሪም ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ በተካሄደው የኑረምበርግ ፍርድ ቤት (Nuremberg Trials)፣ «ደስ ስቱርመር» በተባለው ጋዜጣ የናዚን የጥላቻ ፕሮፓጋንዳ ያሰራጭ የነበረው ጁሊየስ ሺራይቸር፣ በቀጥታ የጦር መሳሪያ ባያነሳም በቃላቱ ባሰራጨው አደገኛ ጥላቻ ምክንያት በሰው ልጅ ላይ ወንጀል በመፈጸሙ ለፍርድ ውሏል።
በተመሳሳይ ሁኔታ ከዩጎዝላቪያ መፍረስ በኋላ በተቋቋመው ዓለም አቀፍ ፍርድ ቤት (ICTY) የፖለቲከኞች እና የብዙኃን መገናኛ ሰዎች አጋጫኝ ንግግሮች በሰብዓዊነት ላይ የተፈጸሙ ወንጀሎች ተደርገው ተወስደው ለዓመታት ተከታትለው ለፍትሕ እንዲቀርቡ ተደርገዋል።
አርቲስት አስቴር በዳኔ «አማራ እና ኦርቶዶክስ የሀገር ባለቤት ነኝ ብሎ ተቀምጧል፤ ቶለሬት የማያደርግ ትውልድ ተነስቶ እየተበቀላቸው ነው» ስትል ያደረገችው ንግግር በሰላማዊ ዜጎች ላይ የሚደርስን ጥቃት እንደ «በቀል» አድርጎ በማቅረብ ወንጀልን የማበረታታት ይዘት ያለው በመሆኑ በዲጂታል ዘመን ማናቸውም የማህበራዊ ሚዲያ ንግግሮች እና መረጃዎች በቀላሉ የማይጠፉ የታሪክ ሰነዶች ናቸው።
ፍትሕ እና የሕግ የበላይነት ሙሉ በሙሉ በሚሰፍንበት ጊዜ እነዚህ ንግግሮች ማህበረሰብን ለጥቃት አጋልጠዋል በሚል በሕግ ፊት የመጠየቂያ ማስረጃዎች መሆናቸው አይቀሬ ነው።
ከሁሉም በላይ ደግሞ ማንኛውም ዜጋ ወይም ማህበረሰብ «የሀገሬ ባለቤት ነኝ» ብሎ ማሰቡና መናገሩ ህገ-መንግስታዊ እና ዜጋዊ መብቱ እንጂ በፍጹም ወንጀል ሊሆን አይችልም።
ይህንን ዜጋዊ መብት እንደ «የበላይነት ጥያቄ» አድርጎ በመተርጎም፣ በሰላማዊ ሰዎች ላይ የሚደርሰውን ግፍና ጥቃት እንደ «ተገቢ የበቀል እርምጃ» አድርጎ ማቅረብ ግን ነገ ምንይዞ እንደሚመጣ ታሪክ ይፈርዳል
በቃላት የሚዘራ ጥላቻ በሰዎች ህይወት ላይ ጥፋት ያመጣል ዛሬ በስሜት ወይም በኃይል አሰላለፍ ተሸፍነው የሚያልፉ ይመስሉ እንጂ በሕግ እና በፍትሕ ስርዓት ውስጥ የጥላቻ ንግግሮች ጊዜ አይሽራቸውም።
አርቲስቶች እና ታዋቂ ሰዎች የሚናገሩት እያንዳንዱ ቃል ነገ በፍርድ ቤት እና በታሪክ ፊት እንደሚያስጠይቅ ተረድተው ከህዝብ አጋጫኝ ንግግሮች ሊቆጠቡ ይገባል።
Sponsored by
Surafel
Comments