10 hours ago
መዝሙረ ሄላም ላይ የተደረገ አጭር ኂሳዊ ንባብ
ከቢኒያም አቡራ
#ethiopia | አዳም ረታ ታሪክን ከነገሥታት፣ ከመሪዎች፣ ማኅበረሰቡ ባበጀው ድልድል ውስጥ ‹ላዕላይ› ከሚባሉት ደረጃዎች አንጻር አያስመለክተንም። ታሪካዊ ከሚባሉ አጋጣሚዎች ውስጥ የተዘነጉትን ጥቃቅን የታሪክ ኹነተ-ደቂቅ (micro-events) ይመርጣል። ይወስዳል መንገድ ላይ … “ቀዳዳ” በተሰኘው ታሪክ ላይ ፍንዳታውን ከሚሞት ዘመድ፣ ከሚደነግጥ ለማኝ፣ ከሚሰነጠቅ የወፍ እንቁላል፣ ከሚፈስ የእናት ወተት ጋር Micro-Macro Connection በመፍጠር የትልቁ ቀዳዳ መፈጠርን ከሚጢጢዬ ሽንቁሮች ጋር ያስተሳስርልናል። እንዲህ ያሉ የኒው ሂስቶሪሲዝም ባሕሪያትን ከዚህ ቀደም ባሳተማቸው መጻሕፍቱ ውስጥ በተለያየ መጠን እናገኛለን።
Adam Reta አዳም ረታ "መዝሙረ ሄላም" በተሰኘው በዐዲሱ መጽሐፉ ላይም በኢትዮጵያ ታሪካዊ-ፖለቲካዊ አጋጣሚ ውስጥ እንደ ዐውራ የሚታዩትን የእድገት በኅብረት ዘመቻን እንደነ-አሮን፣ እንደነቃል … ባሉ ገጸባሕርያት በኩል፣ የሰባ ሰባቱን ድርቅ በሄላም ጡት በኩል፣ “ጥላሁን ለምን ለምን ሞተ” እየተባለ ኢዮቤልዩ ቤተመንግሥት ጋር የተደረገውን ሰላማዊ ሰልፍ በሡልጣን በኩል፣ የከተማ መሬት ዐዋጅን በተለያዩ ግለሰቦች በኩል … እናያለን። በዚህም የታሪክን ትልቅ ካርታ ለመረዳት የተረሱና የጠለሉ ታሪኮችን ይመረምራል። ስለዚህ ነቁጣዊ ማኅበራዊ ክስተቶችን ወደ ታሪክ ምኩራብ በማምጣት ከትልቁ የታሪክ ምሥል ጎን ያስተያያል። ይህ ደግሞ የኒው ሂስቶሪሲዝም ኹነኛ ማጠንጠኛ ነው።
ልክ “ይወስዳል መንገድ ያመጣል መንገድ …” በተሰኘው መጽሐፉ ውስጥ ባለው “የመንግሥቱ ጊዜ” በሚለው ድርሰት ውስጥ፣ ትልቁን “የታኅሣሥ ግርግር”ን እንደ መቼት አምጥቶ የተጻፈውና የተተኮረው ግን ኹነተ-ደቂቅ (micro-events) ላይ ነው። ስለግርማሜ ንዋይ፣ ስለኮሌኔል ወርቅነህ ገበየሁ፣ ሰለጄነራል ሙልጌታ ቡሊ አይደለም የሚያትተው። ስለአንድ ብላቴና ከእንቅልፍ መነሳት፣ ስለገበጣ ጨዋታ፣ ቤተክርስቲያን ውስጥ ሕፃናትን አሰብስቦ ‹ኪራላይሶን› የሚያስብል ካሕን፣ ስለመንደር ውስጥ ሐሜቶች፣ ስለግለሰቦች ፍርሃት፣ በአጋጣሚ ስላየው አስደናቂ አሞራ … ያወጋል። የታሪክ አጋጣሚ አምጥቶ በታሪክ ውስጥ ግለሰቦች ላይ ስለሚረብበው የታሪክ መንፈስ ያትታል። ልክ እንደዚሁ መዝሙረ ሄላም ላይም ጽሑፉ ታሪክን አያብራራም፤ ነገር ግን ታሪክ እንዴት በሰው ልብ ውስጥ እንደሚኖር ያሳያል። በዚህ ኹነተ-ደቂቅ (micro-event) ምክንያት በዘመኑ ላይ ያገነገነውን ባሕላዊ እምነትን፣ የሥልጣን መዋቅርን፣ የወል ግንዛቤን አጨንቁረን እንድንመለከት ያስችለናል።
ከመንግሥት ሼልፍ ላይ ሳይኾን ከግለሰብ ጀርባ ላይ የተወሰደው የአዳም የአጻጻፍ መንገድ ከኒው ሂስቶሪስዝም ጽንሰ-ሐሳቦች ጋር በአንድ መም ላይ የሚሄዱ ናቸው። መዝሙረ ሄላም የተሰኘው ዐዲሱ የአዳም ረታ መጽሐፍ የኒው ሂስቶሪሲዝም ባሕርያትን ይጋራል። አንዳንድ ነገሮችን በዓይን መመልከት ባይቻልም በግብሩ (ቁስ ላይ በሚያደርገው ግፊት) ግን ይታወቃል። በመዝሙረ ሄላም መጽሐፍ ውስጥም አንዳንድ ነገሮችን በቀጥታ ማየት ባንችልም ቅሉ እነርሱን የሚያሳይልንን ነገሮች ግን እንቃኛለን። ዘማች ወጣት ተማሪዎችን እናያለን፤ መንግሥትን፣ ሕግንና ኃይልን ግን በቀጥታ አንመለከትም። የተማከለ ኃይል አናይም ግን የገጸባሕርያቱ የፍርሃት ምንጭ ከተማከለ ኃይል ጋር የተያያዘ ቀጭን መስመር መኖሩን እናያለን። መንግሥትም ቢኾን በቀጥታ አይገባም፤ ነገር ግን ፍርሃት እንደ ሥርዓት ዘዋሪ (system driver) ይኾናል። እንደ ሚሸል ፉኮ አገላለጽ ኃይል ከተማከለ ሥርዓት የሚመነጭ ሳይኾን በየትኛውም ቦታና ጊዜ በፍርሃት፣ በልማድ፣ በንግግር … ሊከሰት የሚችል ሂደት አይደል?
መዝሙረ ሄላም ላይ ታሪክ እንደ “circulation of social energy” ቀርቧል። መዝሙረ ሄላም ላይ መረጃ ከመንግሥት አይመጣም፤ ከግለሰብ እንጂ። የከተማ መሬት ዐዋጅም ኾነ የተማሪዎች ዘመቻ በገጸባሕርያቱ ወሬ ውስጥ ነው የሚንቀረቀበው። ይህ የመረጃ ሥርዓት ኃይል ማን እንዳለው ማን እንደሌለው ያሳያል። እንግዲህ ይህ በፉኮኛ micro-power መኾኑ ነው። በመዝሙረ ሄላም ላይ ታሪክ እንደ ወሬ እንጂ እንደ ሰነድ አይቀርብም።
ወሬ የፍርሃት ቤንዚን ነው … ፍርሃት ደግሞ በዝምታ መሸበብን ይፈጥራል … የዝምታ አፈ-ሙቅ ደግሞ ኃይለኛው እንዳይታይ ያደርጋል … የተደራጀው ኃይል ጥፋትን ሊያደርስ ባሰበ ቁጥር የወሬ ቤንዚን ይጨምራል። ሰዎች በዕቅብተ-ንግግር ራሳቸውን ሲሸብቡ ደርዝ ያለው ሙግት ይኮሰምናል፣ ንግግር ሲጠፋ ያልታወቀ አደጋ ይከሰታል፣ ፍርሃትም ይጨምራል። ያልታወቀ አደጋ ደግሞ ከታወቀ አካል ይመጣል። ስለዚህ ጥንስሱ የሚጀምረው ከወሬ እንደኾነ ያስመለክተናል። አዳም በመዝሙረ ሄላም ላይ ታሪክን እንደ “circulation of social energy” ሲያቀርብ ፕሬዝዳንት፣ ጀነራል፣ ፕሮፌሰር የኾኑ ታሪክ ከላዕላይ ያስቀመጣቸው ሰዎች አያስፈልጉትም። በአንጻሩ ሄላም ለማን እንደሳመችው ተደርጎ ብርሃኔ ያስወራው ወሬ፣ የሄላም አባት ወታደር በመኾኑ ምክንያት በካሱ፣ በሄኖክ እናት የተነዛው ወሬ እና ሄላም ከሄኖክ ጋር የተቆራረጠችበት መንገድ እንዲሁም የሄላምን የጡት ወተት በተመለከተ የተነዛው ወሬን ይጠቀማል።
መዝሙረ ሄላምን ከድኅረ-ቅኝ-አገዛዝ የኂስ መንገድ አንጻር እንመልከተው።
እውን ቅኝ-ግዛት ተረት ኾኖ ቀርቷል? በፖለቲካ፣ በኢኮኖሚ፣ በሥነልቦና ረገድ የቅኝ አገዛዝ ዳናው ሙሉ ለሙሉ ጠፍቷል? አዳም በመዝሙረ ሄላም ጽሑፍ ውስጥ ከቅኝ-ግዛት በተወረሰ መዋቅር ምክንያት የተሰናከለን ሕይወት ሊያስመለክተን ይኾን?
“ከተሞች ከቅኝ ግዛት በኋላ ሁለት ዓይነት መልክ ይኖራቸዋል፤ ለጥቂቱ የተድላ፣ ለተቀረው ደግሞ የአሳር መንደር ይኾናሉ” ይላል ፍራንዝ ፋኖን። በመዝሙረ ሄላም ላይ እና “የቢሾፍቱ ልጆች ጥላሞት” የተሰኘው ድርሰት ላይም ይህንን ነው የምንመለከተው። “ይወስዳል መንገድ ያመጣል መንገድ …” በተሰኘው መጽሐፉ ውስጥ ካሉ ጽሑፎች መካከል “የቢሾፍቱ ልጆች ጥላ ሞት” አንዱ ነው። የቢሾፍቱ ልጆች ሆቴሉን ያዩታል፤ ግን አይገቡበትም። ሆቴሉ የሀገራቸው መሬት ላይ ነው፤ እነርሱ ግን ከሆቴሉ ውጭ ናቸው። መናፈሻው ውስጥ አንዲት የፈረንጅ ልጅ ጠግባ ለልጆቹ እንደ ውሻ ዳቦ ትወረውርላቸዋለች። አፈር ላይ የወደቀን ዳቦ አራግፈው ይመገባሉ። በገዛ ሐይቃቸው ዳር ላይ ናቸው፤ ሌሎች ግን በጀልባ እየተንሸራሸሩ ይንፈላሰሳሉ። ለፈረንጆቹ ያደረው ሞገስ የላንድሮቨር ተፈናጣጭ ኾኗል። ሌሎቹ ግን ከመኪናው ውጪ ናቸው። ሞገስ እንደ እነርሱ ሕጻን ቢኾንም ለፈረንጅ በማሸርገዱ የትምህርት ቤቱ ባለቤት ሲመስል ሌሎች ልጆች ግን በገዛ መምህራቸው ይብጠለጠላሉ። የቢሾፍቱ ልጆች፣ ነጻ በተባለች ሀገር እየኖሩ በቅኝ ግዛት ጥላ ይተዳደራሉ። የቢሾፍቱ ልጆች በገዛ መንደራቸው አካሉ በማይታይ የቅኝ ግዛት እጅ ይገፋሉ። ሞገስ አይናገርም፤ የሚናገርለት አለ። ልክ የቢሾፍቱ ልጆች ላይ በአንድ ከተማ ውስጥ ሁለት የከተማ ምሥል እንደምናገኘው ሁሉ “የስንብት ቀለማት” ላይም በአዲስ አበባ ውስጥ ሁለት የከተማ ምሥል እንመለከታለን። እንደ ዘድሬክ፣ ሳተርን፣ ከተስፋዬ ወደ አሸናፊ የተቀየሩ የድሎት ምሥሎች እና የእነምትክ ጉልት፣ የእትየ እልልታ የጉርሻ መሸጫ መስኮት ያሉ የእጦት ሥዕል እናገኛለን። መዝሙረ ሄላም ላይም እንዲህ ያለ በአንድ ከተማ ላይ የሁለት ምሥሎች አደባባይ እጀግ ብዙ ቦታ ይገኛል።
በሌላኛው የድኅረ-ቅኝ-ግዛት ኂስ (postcolonial criticism) መዝሙረ ሄላምን ስንመለከት መጀመሪያ ላይ “ፈረንጅ ሲያደንቀኝና ሲገረምብኝ የሰሙ የአገሬ ደነዞች በየተራ “ካላስ የኔ ጎሳ ናት” … እያሉ መሻማት ጀመሩ ትላለች - ሄላም። በኋላ ደግሞ በተነዛባት አጓጉል ወሬ … የሄላምን ጡት ንቀው፣ አንጓጥጠው፣ አባረዋት ሲያበቁ የፈረንጅ የዱቄት ወተትን ይመርጣሉ። ይህ በባሕላዊ ማንነትና በዘመናዊነት መካከል የሚዋልል ማኅበረሰብን ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ የድኅረ-ቅኝ-ግዛት አካል ነው። በሌሎቹ የአዳም ሥራዎች ውስጥ ድኅረ-ቅኝ-ግዛት አተያይ በቋንቋና በኪነ-ጥበብ ምርጫ ውስጥ እንዴት እንደሚንፀባረቅ ያሳያል። በመዝሙረ ሄላም ላይ ደግሞ ምዕራባዊው ዓለም ለአገር በቀል መፍትኼ-ሥራይ የሚሰጠው ዋጋ ዝቅተኛ መኾኑንና የኢኮኖሚ ብዝበዛው አሁንም በረቂቅ መንገድ መቀጠሉን ያሳያል። እዚህ ላይ ሥዕለማርያም የተባለችዋን ገጸባሕርይ እና በውጭ ሀገራት የተነዙ ወሬዎችን ስንጨማምር ደግሞ የበለጠ ብዙ ለማለት ያስችላል።
መዝሙረ ሄላም ላይ እጅግ ብዙ ማኅበረሰባዊ ኂስ እናገኛለን። ለአብነት ያህል አንድ ሁለቱን እንቃኝ።
“መዝሙረ ሄላም” ላይ ማኅበረሰቡ በችላ-ባይነት አልያም በኾን ተብሎነት ልጆቹን ምን ያህል ተጠቂ እንዳደረጋቸው የሚያሳይ መልክ ተንጸባርቆበታል ማለት ይቻላል። ጋሽ ክብካብና ዘመናይ ኾን ብለው ቴዲና ሄላም ላይ የሚያደርሱትን፣ ተክለማርያም የወላጁን(የዘሪቱን) ችላ-ባይነት ለአብነት ማቅረብ ይቻላል። ማኅበረሰቡ ልጆችን “የነገ ተስፋዎች” ይላል፤ ነገር ግን ዛሬያቸው ላይ አይሠራም።
ማኅበረሰብ የመማጸኛ ከተማዎችን ወደ ተጨማሪ ግፍ መሥሪያ ቦታዎች እንደሚቀይር በአዳም መጻሕፍት ላይ በብዛት እንመለከታለን። “ይወስዳል መንገድ …” ላይ … “ቀዳዳ” በተሰኘው ታሪክ ላይ ማርታ ለደበበ በምትሰጠው ፍቅር ሳቢያ የሚሠራበትን ግፍ የምታስረሳ ብትኾንም ማኅበረሰቡ ግን ተጨማሪ ግፍ የሚሠራበት መሣሪያ ኾናለች። የስንብት ቀለማት ላይ ምኒልክ ከዚያ ሁሉ እስርና እንግልት በኋላ፣ “በፊያሜታ አርፋለሁ” ብሎ ቤቷ ሲሄድ ተጨማሪ ሕመም በጆሮው በኩል ጭንቅላቱ ላይ ይሻጥበታል። መዝሙረ ሄላም ላይም፣ ሄላም “ሙዚቃዬን ከሕዝብ ጆሮ ያደርስልኛል … ያሳርፈኛል …” ብላ የተመካችበት ምናሴ እንጦሮጦስ ይጨምራታል። ማኅበረሰባችን የመስቀል ተ ሠላጢን ግብር እንዳለው፣ ከላይ አሳልሞ ከታች በአንካሴው ጉድጓድ እንደሚምስ ያሳያል። ይህም የመልእክትን ወጭት ሰብሮ የወጣ ጥበባዊ አጻጻፍ ነው። በፈጣጣው የቀረበ የትችት ኮሶ አይደለም። ድንቅ ነው!
መዝሙረ ሄላም ላይ ከምናገኛቸው ዋና ዋና ገጸባሕርያት የተወሰኑት (አሮን፣ ቃል፣ ምናሴ፣ ሄላም) ላይ መጠነኛ ቅኝት እናድርግ።
auto-fiction ዓይነት አጻጻፍ ባለው የአሮን አተራረክ ውስጥ አሮን “system observer” መኾኑን እንገነዘባለን። ሥርዓቱን ያያል፣ ዘማቹን ያስተውላል፣ ቃለጉባኤ ይይዛል፣ ችግሩን ይመለከታል፣ ይጽፋል። አሮን የተገፋ ታሪክ ድምፅ ነው፤ ንቃት አለው፣ ግን የታሪክ ሂደትን የሚቀይር ኃይል የለውም፤ ስለዚህም ያ ሁሉ የጻፈውን ጽሑፍን ያጣል። የንቃት ችግር የለበትም፤ የማኅበራዊ ንቃት ድምፅነቱን ከዘመነ አባት ጋር ባደረገው ውይይት ውስጥ ተመልክተናል። ግን ደግሞ ይህ ብቻውን የቆመ ነጠላ ነገር ነው፤ ምክንያቱም ማኅበራዊ ተሳትፎ የለበትም። ቃል የተሰኘችው ገጸባሕርይም እንደ አሮን ናት፤ ንቃት ያላት፣ system observer ናት። ማኅበራዊ ንቃት ማኅበራዊ እንቅስቃሴ ካላገዘው ግንጥል ጌጥ ነው። ቃልና አሮን ንቃት አላቸው፤ ግን ንቃታቸውን ተግባር አላገዘውም፤ ንቃቱን የሚተገብር አደረጃጀት የላቸውም። ስለዚህ ዕጣ-ፈንታቸው ውድቀት ይኾናል። በኢትዮጵያ ውስጥ የተንሰራፋውን ይህን የድግግሞሽ አዙሪት መዝሙረ ሄላም ላይ ደራሲ አዳም ረታ በሰላ ብዕር አስቀምጧል።
የደራሲና የአርታኢ ትስስር በተንጸባረቀበት በሄላም አተራረክ ውስጥ ምናሴ የተሰኘ ገጸባሕርይ እናገኛለን። ምናሴ የ-false collective consciousness ትእምርት ነው። ምናሴዎች ለሥልጣን ይሠራሉ፣ ራሳቸውን እንደ ነጻ ያስባሉ፤ ነገር ግን የሥርዓቱ የመጠቀሚያ መሣሪያ (system functionary) ናቸው። ምናሴዎች የኦልቪቴዎች ጥይት ናቸው። ምናሴዎች የሔላምዎች ስኬት ሳይኾን የገዛ ጥቅማቸውን የሚያስቀድሙ የማኅበረሰቡ አካል ናቸው። ምናሴ በሌላ መነጽር ብናየው የመንግሥት ቢሮክራት የመካከለኛው መደብ ውክል ነው። ሀገሩ ከንጉሣዊ ሥርዓት ወደ ወታደራዊ ሥርዓት ቢቀየርም፤ ከወታደራዊ ሥርዓት ወደ ሌላ ሥርዓት ቢለወጥም ምናሴያውያን ግን አይቀየሩም። ሥርዓት ይቀየራል - ምናሴያውያን አይቀየሩም፣ ትእዛዝ ይፈጽማሉ፣ ይከድራሉ። ይህ በኢትዮጵያ ፖለቲካል-ታሪክ ውስጥ የተደጋገመ፣ ግን ደግሞ ያልተስተዋለ እውነት ነው።
ሄላም የወታደር ልጅ ናት፤ እንዲያሳድጋት በአደራ የተሰጠው ቤተሰብ የሚበድላት። የሷ ዓይነት ዕጣ ከደረሰው እንደ ወንድሟ ከምታየው ቴዲ ከሚባል ልጅ ጋር ታድጋለች። መጀመሪያ የሚልዮን፣ የኋላ ኋላ የምናሴ ፍቅረኛ የምትኾን ድምፀ-መረዋ ሴት ናት። ሁሉ ነገሯን ባጣችበት ወቅት ጡቷ ተአምር ያመርታል።
በመዝሙረ ሄላም ላይ የሄላም የጡት ወተት የአንዳች ነገር ውክል ይመስለኛል። ሻዕቢያ ለታጋይ ወጣቶች ማሳደጊያ ፈልጓት ሊሰርቃት መፈለጉ በቀላሉ የሚዘለል ነገር ነው? ወተት እና ጡት በመጀመሪያ እይታ የሕፃናት ትዝታ፣ የእናትነት ምሥል፣ የእምነት እና የጾታ መነሳሳት የተዋሃዱበትም አይደል? ወተት ሕይወት ነው? የመጀመሪያ ምግብ፣ ከእናት ወደ ልጅ የሚፈስም አይደል? በክርስቲያናዊ ምልክት ንጹሕነትን አይወክልም? ወተት ከ“ቅዱስ” ወደ “ሥጋዊ” የሚያስተላልፍ ድልድይ ነው ማለት እንችል ይኾን? የሄላምን ጡት የጠባ ታማሚ ልጅ እንዴት ጤናማ ሊኾን ቻለ? የምን ትእምርት ነው? ሄላም ከብዙ ወንድ ጋር የወጣች እንደመኾኗ ለዚህ ሰናይ ግብር ለምን የሷ ጡት ተመረጠ?
ሌላው፣ መዝሙረ ሄላም ላይ ኦልቬቲን እናገኛታለን። ኦልቬቲ የግራጫ ቃጭልዋ። መዝገቡ ንፋስ መውጫ ሳለ፣ ባልንጀራው ኤልያስ የብልግና ሀሁ ሊያስተምረው እፊቱ ያቆማት ቀይ ሰሌዳ ነበረች ኦልቬቲ። መዝሙረ ሄላም ላይ ምናሴን እና ቤተሰቡን የምታሾር ዐውራ ገጸባሕርይ ኾና ትከሰታለች። መዝሙረ ሄላም እና ግራጫ ቃጭሎች በጋለሞታይቱ በኦልቬቲ ብቻ ሳይኾን በዘመነ እንድርያስ እና በመዝገቡ ዱባለም ይገናኛሉ። ነጋ ዳቦ ጋጋሪውም በ-typological space መዝሙረ ሄላም ላይ እናገኘዋለን።
መዝሙረ ሄላምን ከህላዌነት (Existentialism) አንጻር እንመልከተው። ሄላም ትርጉም በማይሰጥ ዓለም ውስጥ እንዴት እንደምትኖር እናነባለን። የሀገሯ ዳር ድንበር እንዳይነካ አባት ብታዋጣም አሳዳጊዎቿ ግን የወላጅን ፍቅር አዋጥተው አይለግሷትም። ወርቅ አበድራ ጠጠር ትነፈጋለች። ዕቃ ለማገዝ ቤቷ ድረስ ለመጣው ሚልዮን ልቧን ትሰጣለች። ሀና የሸነቆረችውን ክፍተት ለሞላችበት ውለታዋ ክፍያ ይኾን ዘንድ ሚልዮን ለሄላም የወለፈንዴ ቡጢ ያሳርፍባታል። ለሕይወት ትርጉም ለመስጠት ባስ ውስጥ ካገኘችው ሄኖክ ጋር ብትሞክርም የበለጠ የሕይወት ትርጉም ይዛባባታል። የወታደር ልጅ መኾኗ ሄላምነቷን በዜሮ ያባዘዋል። የመጨረሻው ስንብትም ከሄኖክ ጓደኛ አፎት በሚወጣ ሰይፍ መቀላት ይኾናል። ከሄኖክ ጓደኛ ጀርባ የሚውለበለበው ባንዲራ ደግሞ የሄኖክ ሸሚዝ መኾኑ ደግሞ ቁስሉን እንደ አቡሰዲቅ ያደርገዋል። ለሕይወቷ ትልቅ ትርጉም ያለውን የሙዚቃ ሥራዋን፣ “ትርጉም ወዳለው
ነገር ይቀይርልኛል” ብላ በምትተማመንበት በምናሴ ትነጠቃለች። ተአምር በሚያስብለው በጡት ወተት ምክንያት ለሕይወቷ ትርጉም ለመስጠት ትታትራለች። የጡት ወተቷን ምርምር በማድረግ ለትልቅ ዓለምአቀፍ በጎ ተፅዕኖ ታደርጋለች ተብላ የተቆጠረችው ሥዕለማርያም የዓለም አቀፍ መሳለቂያና ትችት ምንጭ ትኾንባታለች። ይህ ሁሉ ትርጉም የሌለው ድግግሞሽ ነው። ይህ ደግሞ በሳርተር የተገለጸውን “existence without essence”-ን ያሳያል።
የህላዌነት መሠረታዊ ሐሳብ ነጻነት ነው፤ ግን ነጻነት ፍርሃትን ይወልዳል። ሄላም ለአሮን ፍቅሯን መናገር ትችላለች፤ ነገር ግን ዝምታን መርጣለች። የግራጫው መዝገቡ፣ የእንጀራ እናቱ የምታደርስበትን በደል እንደሚያውቀው ሁሉ ሄላምም ክብካብና ዘበናይ የሚያደርሱባትን አድሎ ታውቃለች፤ ግን ለረዥም ጊዜ ዝም ብላለች። ሄላም፣ ሙዚቃዋን ካጣች በኋላ ወደ ባንዱ ሄዳ መጋፈጥ ትችላለች፤ ነገር ግን አትሄድም … ይህ በሳርተርኛ bad faith ነው።
የሄላም ምርጫ ዝምታ ኾነ እንጂ ደካማ ናት ማለት አይደለም። “አልተናገርኩም ማለት አላውቀውም ማለት አይደለም” የሚል ዝምታ ነው ያላት። በሌላ ጎኑ ደግሞ ዝምታዋ፣ የለመደችውን ግፍ ከማታውቀው ዐዲስ ግፍ የመምረጥ ኹኔታ ነው። ዐዳዲስ ግፎችን ለመሸሽ በዝምታ አላዋቂነት ዛጎል ውስጥ የመደበቅ ብቃት ነው። የለመደችውን ግፍ የመከላከል አቅም ስላላት ባለመደችው ግፍ እንዳያጠፏት ሠግታ በውስጣዊ ንቃተ ሕሊና የዘየደችው ብልሃት ሊኾን ይችላል። ዝምታዋ የመቆየቷ ምሥጢር ነው። ደበበ ቀዝቃዛ ገለልተኛ ነኝ የሚለው ሰው ለመኖር ሲል ሳይታወቀው ስሜቱን የሚቆጣጠርበት መንገድን ለማስታወስ ነው።
“የስንብት ቀለማት” ገጸባሕርይ የኾነው ዮሴፍም ብዙ ነገር ያውቃል፤ ግን ዝም ይላል … ፊያሜታ ቂል መስሏት ትዘባርቃለች … እሱ ግን “አልተናገርኩም ማለት አላውቀውም ማለት አይደለም” የሚል የዝምታ መልስ ይመልስላታል። እሷ ግን ዝምታው አይገባትም። የ“ቀዳዳ”ው ደበበ እና “የስንብት …” ዮሴፍ ቀዳዳውን አይሞሉትም፤ እያዩት ይኖራሉ። ዶነሮች ጥሩ ፈንድ ሲለቁ ፊያሜታ ፕሮጀክቱን ለአሳምነው ትሰጠውና ዮሴፍን “ምን ዶነሮች እኮ ጠፉ ትለዋለች” … ዝም ይላል፤ ይታዘባል።
ቃል መሣሪያ ነበር፤ በዘመነ ደበበ፣ በዘመነ ዮሴፍ፣ በዘመነ ሄላም እና በዘመነ መዝገቡ ዱባለ ግን ቃል አደገኛ ኾኗል፤ ዝምታ ኹነኛ መጠጊያ ነው … ይህ ከደርግ በኋላ የተፈጠረ “traumatized literary silence” ማሳያ ነው። ስለኾነም ተራኪዎቹ (ደበበ፣ መዝገቡ፣ ዮሴፍ እና ሄላም) ለምን ዝም አሉ ሳይኾን "ዝምታን የሚያመነጭ ሥርዓት ምን ይኾን?" ብለን እንድንጠይቅ ያደርጋል። ግለሰብ ዝም ሲል፤ ሕዝብ በጸጥታ ይዋጣል፤ የዚያኔ የተማከለው ኃይል አፍ ያወጣል።
የአዳምን ዐዲሱን መጽሐፍ "በንባብ ይለቅ" ብለን መርቀናል።
ቢኒያም አቡራ
ሐምሌ 25 / 2018 ዓ.ም
ከቢኒያም አቡራ
#ethiopia | አዳም ረታ ታሪክን ከነገሥታት፣ ከመሪዎች፣ ማኅበረሰቡ ባበጀው ድልድል ውስጥ ‹ላዕላይ› ከሚባሉት ደረጃዎች አንጻር አያስመለክተንም። ታሪካዊ ከሚባሉ አጋጣሚዎች ውስጥ የተዘነጉትን ጥቃቅን የታሪክ ኹነተ-ደቂቅ (micro-events) ይመርጣል። ይወስዳል መንገድ ላይ … “ቀዳዳ” በተሰኘው ታሪክ ላይ ፍንዳታውን ከሚሞት ዘመድ፣ ከሚደነግጥ ለማኝ፣ ከሚሰነጠቅ የወፍ እንቁላል፣ ከሚፈስ የእናት ወተት ጋር Micro-Macro Connection በመፍጠር የትልቁ ቀዳዳ መፈጠርን ከሚጢጢዬ ሽንቁሮች ጋር ያስተሳስርልናል። እንዲህ ያሉ የኒው ሂስቶሪሲዝም ባሕሪያትን ከዚህ ቀደም ባሳተማቸው መጻሕፍቱ ውስጥ በተለያየ መጠን እናገኛለን።
Adam Reta አዳም ረታ "መዝሙረ ሄላም" በተሰኘው በዐዲሱ መጽሐፉ ላይም በኢትዮጵያ ታሪካዊ-ፖለቲካዊ አጋጣሚ ውስጥ እንደ ዐውራ የሚታዩትን የእድገት በኅብረት ዘመቻን እንደነ-አሮን፣ እንደነቃል … ባሉ ገጸባሕርያት በኩል፣ የሰባ ሰባቱን ድርቅ በሄላም ጡት በኩል፣ “ጥላሁን ለምን ለምን ሞተ” እየተባለ ኢዮቤልዩ ቤተመንግሥት ጋር የተደረገውን ሰላማዊ ሰልፍ በሡልጣን በኩል፣ የከተማ መሬት ዐዋጅን በተለያዩ ግለሰቦች በኩል … እናያለን። በዚህም የታሪክን ትልቅ ካርታ ለመረዳት የተረሱና የጠለሉ ታሪኮችን ይመረምራል። ስለዚህ ነቁጣዊ ማኅበራዊ ክስተቶችን ወደ ታሪክ ምኩራብ በማምጣት ከትልቁ የታሪክ ምሥል ጎን ያስተያያል። ይህ ደግሞ የኒው ሂስቶሪሲዝም ኹነኛ ማጠንጠኛ ነው።
ልክ “ይወስዳል መንገድ ያመጣል መንገድ …” በተሰኘው መጽሐፉ ውስጥ ባለው “የመንግሥቱ ጊዜ” በሚለው ድርሰት ውስጥ፣ ትልቁን “የታኅሣሥ ግርግር”ን እንደ መቼት አምጥቶ የተጻፈውና የተተኮረው ግን ኹነተ-ደቂቅ (micro-events) ላይ ነው። ስለግርማሜ ንዋይ፣ ስለኮሌኔል ወርቅነህ ገበየሁ፣ ሰለጄነራል ሙልጌታ ቡሊ አይደለም የሚያትተው። ስለአንድ ብላቴና ከእንቅልፍ መነሳት፣ ስለገበጣ ጨዋታ፣ ቤተክርስቲያን ውስጥ ሕፃናትን አሰብስቦ ‹ኪራላይሶን› የሚያስብል ካሕን፣ ስለመንደር ውስጥ ሐሜቶች፣ ስለግለሰቦች ፍርሃት፣ በአጋጣሚ ስላየው አስደናቂ አሞራ … ያወጋል። የታሪክ አጋጣሚ አምጥቶ በታሪክ ውስጥ ግለሰቦች ላይ ስለሚረብበው የታሪክ መንፈስ ያትታል። ልክ እንደዚሁ መዝሙረ ሄላም ላይም ጽሑፉ ታሪክን አያብራራም፤ ነገር ግን ታሪክ እንዴት በሰው ልብ ውስጥ እንደሚኖር ያሳያል። በዚህ ኹነተ-ደቂቅ (micro-event) ምክንያት በዘመኑ ላይ ያገነገነውን ባሕላዊ እምነትን፣ የሥልጣን መዋቅርን፣ የወል ግንዛቤን አጨንቁረን እንድንመለከት ያስችለናል።
ከመንግሥት ሼልፍ ላይ ሳይኾን ከግለሰብ ጀርባ ላይ የተወሰደው የአዳም የአጻጻፍ መንገድ ከኒው ሂስቶሪስዝም ጽንሰ-ሐሳቦች ጋር በአንድ መም ላይ የሚሄዱ ናቸው። መዝሙረ ሄላም የተሰኘው ዐዲሱ የአዳም ረታ መጽሐፍ የኒው ሂስቶሪሲዝም ባሕርያትን ይጋራል። አንዳንድ ነገሮችን በዓይን መመልከት ባይቻልም በግብሩ (ቁስ ላይ በሚያደርገው ግፊት) ግን ይታወቃል። በመዝሙረ ሄላም መጽሐፍ ውስጥም አንዳንድ ነገሮችን በቀጥታ ማየት ባንችልም ቅሉ እነርሱን የሚያሳይልንን ነገሮች ግን እንቃኛለን። ዘማች ወጣት ተማሪዎችን እናያለን፤ መንግሥትን፣ ሕግንና ኃይልን ግን በቀጥታ አንመለከትም። የተማከለ ኃይል አናይም ግን የገጸባሕርያቱ የፍርሃት ምንጭ ከተማከለ ኃይል ጋር የተያያዘ ቀጭን መስመር መኖሩን እናያለን። መንግሥትም ቢኾን በቀጥታ አይገባም፤ ነገር ግን ፍርሃት እንደ ሥርዓት ዘዋሪ (system driver) ይኾናል። እንደ ሚሸል ፉኮ አገላለጽ ኃይል ከተማከለ ሥርዓት የሚመነጭ ሳይኾን በየትኛውም ቦታና ጊዜ በፍርሃት፣ በልማድ፣ በንግግር … ሊከሰት የሚችል ሂደት አይደል?
መዝሙረ ሄላም ላይ ታሪክ እንደ “circulation of social energy” ቀርቧል። መዝሙረ ሄላም ላይ መረጃ ከመንግሥት አይመጣም፤ ከግለሰብ እንጂ። የከተማ መሬት ዐዋጅም ኾነ የተማሪዎች ዘመቻ በገጸባሕርያቱ ወሬ ውስጥ ነው የሚንቀረቀበው። ይህ የመረጃ ሥርዓት ኃይል ማን እንዳለው ማን እንደሌለው ያሳያል። እንግዲህ ይህ በፉኮኛ micro-power መኾኑ ነው። በመዝሙረ ሄላም ላይ ታሪክ እንደ ወሬ እንጂ እንደ ሰነድ አይቀርብም።
ወሬ የፍርሃት ቤንዚን ነው … ፍርሃት ደግሞ በዝምታ መሸበብን ይፈጥራል … የዝምታ አፈ-ሙቅ ደግሞ ኃይለኛው እንዳይታይ ያደርጋል … የተደራጀው ኃይል ጥፋትን ሊያደርስ ባሰበ ቁጥር የወሬ ቤንዚን ይጨምራል። ሰዎች በዕቅብተ-ንግግር ራሳቸውን ሲሸብቡ ደርዝ ያለው ሙግት ይኮሰምናል፣ ንግግር ሲጠፋ ያልታወቀ አደጋ ይከሰታል፣ ፍርሃትም ይጨምራል። ያልታወቀ አደጋ ደግሞ ከታወቀ አካል ይመጣል። ስለዚህ ጥንስሱ የሚጀምረው ከወሬ እንደኾነ ያስመለክተናል። አዳም በመዝሙረ ሄላም ላይ ታሪክን እንደ “circulation of social energy” ሲያቀርብ ፕሬዝዳንት፣ ጀነራል፣ ፕሮፌሰር የኾኑ ታሪክ ከላዕላይ ያስቀመጣቸው ሰዎች አያስፈልጉትም። በአንጻሩ ሄላም ለማን እንደሳመችው ተደርጎ ብርሃኔ ያስወራው ወሬ፣ የሄላም አባት ወታደር በመኾኑ ምክንያት በካሱ፣ በሄኖክ እናት የተነዛው ወሬ እና ሄላም ከሄኖክ ጋር የተቆራረጠችበት መንገድ እንዲሁም የሄላምን የጡት ወተት በተመለከተ የተነዛው ወሬን ይጠቀማል።
መዝሙረ ሄላምን ከድኅረ-ቅኝ-አገዛዝ የኂስ መንገድ አንጻር እንመልከተው።
እውን ቅኝ-ግዛት ተረት ኾኖ ቀርቷል? በፖለቲካ፣ በኢኮኖሚ፣ በሥነልቦና ረገድ የቅኝ አገዛዝ ዳናው ሙሉ ለሙሉ ጠፍቷል? አዳም በመዝሙረ ሄላም ጽሑፍ ውስጥ ከቅኝ-ግዛት በተወረሰ መዋቅር ምክንያት የተሰናከለን ሕይወት ሊያስመለክተን ይኾን?
“ከተሞች ከቅኝ ግዛት በኋላ ሁለት ዓይነት መልክ ይኖራቸዋል፤ ለጥቂቱ የተድላ፣ ለተቀረው ደግሞ የአሳር መንደር ይኾናሉ” ይላል ፍራንዝ ፋኖን። በመዝሙረ ሄላም ላይ እና “የቢሾፍቱ ልጆች ጥላሞት” የተሰኘው ድርሰት ላይም ይህንን ነው የምንመለከተው። “ይወስዳል መንገድ ያመጣል መንገድ …” በተሰኘው መጽሐፉ ውስጥ ካሉ ጽሑፎች መካከል “የቢሾፍቱ ልጆች ጥላ ሞት” አንዱ ነው። የቢሾፍቱ ልጆች ሆቴሉን ያዩታል፤ ግን አይገቡበትም። ሆቴሉ የሀገራቸው መሬት ላይ ነው፤ እነርሱ ግን ከሆቴሉ ውጭ ናቸው። መናፈሻው ውስጥ አንዲት የፈረንጅ ልጅ ጠግባ ለልጆቹ እንደ ውሻ ዳቦ ትወረውርላቸዋለች። አፈር ላይ የወደቀን ዳቦ አራግፈው ይመገባሉ። በገዛ ሐይቃቸው ዳር ላይ ናቸው፤ ሌሎች ግን በጀልባ እየተንሸራሸሩ ይንፈላሰሳሉ። ለፈረንጆቹ ያደረው ሞገስ የላንድሮቨር ተፈናጣጭ ኾኗል። ሌሎቹ ግን ከመኪናው ውጪ ናቸው። ሞገስ እንደ እነርሱ ሕጻን ቢኾንም ለፈረንጅ በማሸርገዱ የትምህርት ቤቱ ባለቤት ሲመስል ሌሎች ልጆች ግን በገዛ መምህራቸው ይብጠለጠላሉ። የቢሾፍቱ ልጆች፣ ነጻ በተባለች ሀገር እየኖሩ በቅኝ ግዛት ጥላ ይተዳደራሉ። የቢሾፍቱ ልጆች በገዛ መንደራቸው አካሉ በማይታይ የቅኝ ግዛት እጅ ይገፋሉ። ሞገስ አይናገርም፤ የሚናገርለት አለ። ልክ የቢሾፍቱ ልጆች ላይ በአንድ ከተማ ውስጥ ሁለት የከተማ ምሥል እንደምናገኘው ሁሉ “የስንብት ቀለማት” ላይም በአዲስ አበባ ውስጥ ሁለት የከተማ ምሥል እንመለከታለን። እንደ ዘድሬክ፣ ሳተርን፣ ከተስፋዬ ወደ አሸናፊ የተቀየሩ የድሎት ምሥሎች እና የእነምትክ ጉልት፣ የእትየ እልልታ የጉርሻ መሸጫ መስኮት ያሉ የእጦት ሥዕል እናገኛለን። መዝሙረ ሄላም ላይም እንዲህ ያለ በአንድ ከተማ ላይ የሁለት ምሥሎች አደባባይ እጀግ ብዙ ቦታ ይገኛል።
በሌላኛው የድኅረ-ቅኝ-ግዛት ኂስ (postcolonial criticism) መዝሙረ ሄላምን ስንመለከት መጀመሪያ ላይ “ፈረንጅ ሲያደንቀኝና ሲገረምብኝ የሰሙ የአገሬ ደነዞች በየተራ “ካላስ የኔ ጎሳ ናት” … እያሉ መሻማት ጀመሩ ትላለች - ሄላም። በኋላ ደግሞ በተነዛባት አጓጉል ወሬ … የሄላምን ጡት ንቀው፣ አንጓጥጠው፣ አባረዋት ሲያበቁ የፈረንጅ የዱቄት ወተትን ይመርጣሉ። ይህ በባሕላዊ ማንነትና በዘመናዊነት መካከል የሚዋልል ማኅበረሰብን ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ የድኅረ-ቅኝ-ግዛት አካል ነው። በሌሎቹ የአዳም ሥራዎች ውስጥ ድኅረ-ቅኝ-ግዛት አተያይ በቋንቋና በኪነ-ጥበብ ምርጫ ውስጥ እንዴት እንደሚንፀባረቅ ያሳያል። በመዝሙረ ሄላም ላይ ደግሞ ምዕራባዊው ዓለም ለአገር በቀል መፍትኼ-ሥራይ የሚሰጠው ዋጋ ዝቅተኛ መኾኑንና የኢኮኖሚ ብዝበዛው አሁንም በረቂቅ መንገድ መቀጠሉን ያሳያል። እዚህ ላይ ሥዕለማርያም የተባለችዋን ገጸባሕርይ እና በውጭ ሀገራት የተነዙ ወሬዎችን ስንጨማምር ደግሞ የበለጠ ብዙ ለማለት ያስችላል።
መዝሙረ ሄላም ላይ እጅግ ብዙ ማኅበረሰባዊ ኂስ እናገኛለን። ለአብነት ያህል አንድ ሁለቱን እንቃኝ።
“መዝሙረ ሄላም” ላይ ማኅበረሰቡ በችላ-ባይነት አልያም በኾን ተብሎነት ልጆቹን ምን ያህል ተጠቂ እንዳደረጋቸው የሚያሳይ መልክ ተንጸባርቆበታል ማለት ይቻላል። ጋሽ ክብካብና ዘመናይ ኾን ብለው ቴዲና ሄላም ላይ የሚያደርሱትን፣ ተክለማርያም የወላጁን(የዘሪቱን) ችላ-ባይነት ለአብነት ማቅረብ ይቻላል። ማኅበረሰቡ ልጆችን “የነገ ተስፋዎች” ይላል፤ ነገር ግን ዛሬያቸው ላይ አይሠራም።
ማኅበረሰብ የመማጸኛ ከተማዎችን ወደ ተጨማሪ ግፍ መሥሪያ ቦታዎች እንደሚቀይር በአዳም መጻሕፍት ላይ በብዛት እንመለከታለን። “ይወስዳል መንገድ …” ላይ … “ቀዳዳ” በተሰኘው ታሪክ ላይ ማርታ ለደበበ በምትሰጠው ፍቅር ሳቢያ የሚሠራበትን ግፍ የምታስረሳ ብትኾንም ማኅበረሰቡ ግን ተጨማሪ ግፍ የሚሠራበት መሣሪያ ኾናለች። የስንብት ቀለማት ላይ ምኒልክ ከዚያ ሁሉ እስርና እንግልት በኋላ፣ “በፊያሜታ አርፋለሁ” ብሎ ቤቷ ሲሄድ ተጨማሪ ሕመም በጆሮው በኩል ጭንቅላቱ ላይ ይሻጥበታል። መዝሙረ ሄላም ላይም፣ ሄላም “ሙዚቃዬን ከሕዝብ ጆሮ ያደርስልኛል … ያሳርፈኛል …” ብላ የተመካችበት ምናሴ እንጦሮጦስ ይጨምራታል። ማኅበረሰባችን የመስቀል ተ ሠላጢን ግብር እንዳለው፣ ከላይ አሳልሞ ከታች በአንካሴው ጉድጓድ እንደሚምስ ያሳያል። ይህም የመልእክትን ወጭት ሰብሮ የወጣ ጥበባዊ አጻጻፍ ነው። በፈጣጣው የቀረበ የትችት ኮሶ አይደለም። ድንቅ ነው!
መዝሙረ ሄላም ላይ ከምናገኛቸው ዋና ዋና ገጸባሕርያት የተወሰኑት (አሮን፣ ቃል፣ ምናሴ፣ ሄላም) ላይ መጠነኛ ቅኝት እናድርግ።
auto-fiction ዓይነት አጻጻፍ ባለው የአሮን አተራረክ ውስጥ አሮን “system observer” መኾኑን እንገነዘባለን። ሥርዓቱን ያያል፣ ዘማቹን ያስተውላል፣ ቃለጉባኤ ይይዛል፣ ችግሩን ይመለከታል፣ ይጽፋል። አሮን የተገፋ ታሪክ ድምፅ ነው፤ ንቃት አለው፣ ግን የታሪክ ሂደትን የሚቀይር ኃይል የለውም፤ ስለዚህም ያ ሁሉ የጻፈውን ጽሑፍን ያጣል። የንቃት ችግር የለበትም፤ የማኅበራዊ ንቃት ድምፅነቱን ከዘመነ አባት ጋር ባደረገው ውይይት ውስጥ ተመልክተናል። ግን ደግሞ ይህ ብቻውን የቆመ ነጠላ ነገር ነው፤ ምክንያቱም ማኅበራዊ ተሳትፎ የለበትም። ቃል የተሰኘችው ገጸባሕርይም እንደ አሮን ናት፤ ንቃት ያላት፣ system observer ናት። ማኅበራዊ ንቃት ማኅበራዊ እንቅስቃሴ ካላገዘው ግንጥል ጌጥ ነው። ቃልና አሮን ንቃት አላቸው፤ ግን ንቃታቸውን ተግባር አላገዘውም፤ ንቃቱን የሚተገብር አደረጃጀት የላቸውም። ስለዚህ ዕጣ-ፈንታቸው ውድቀት ይኾናል። በኢትዮጵያ ውስጥ የተንሰራፋውን ይህን የድግግሞሽ አዙሪት መዝሙረ ሄላም ላይ ደራሲ አዳም ረታ በሰላ ብዕር አስቀምጧል።
የደራሲና የአርታኢ ትስስር በተንጸባረቀበት በሄላም አተራረክ ውስጥ ምናሴ የተሰኘ ገጸባሕርይ እናገኛለን። ምናሴ የ-false collective consciousness ትእምርት ነው። ምናሴዎች ለሥልጣን ይሠራሉ፣ ራሳቸውን እንደ ነጻ ያስባሉ፤ ነገር ግን የሥርዓቱ የመጠቀሚያ መሣሪያ (system functionary) ናቸው። ምናሴዎች የኦልቪቴዎች ጥይት ናቸው። ምናሴዎች የሔላምዎች ስኬት ሳይኾን የገዛ ጥቅማቸውን የሚያስቀድሙ የማኅበረሰቡ አካል ናቸው። ምናሴ በሌላ መነጽር ብናየው የመንግሥት ቢሮክራት የመካከለኛው መደብ ውክል ነው። ሀገሩ ከንጉሣዊ ሥርዓት ወደ ወታደራዊ ሥርዓት ቢቀየርም፤ ከወታደራዊ ሥርዓት ወደ ሌላ ሥርዓት ቢለወጥም ምናሴያውያን ግን አይቀየሩም። ሥርዓት ይቀየራል - ምናሴያውያን አይቀየሩም፣ ትእዛዝ ይፈጽማሉ፣ ይከድራሉ። ይህ በኢትዮጵያ ፖለቲካል-ታሪክ ውስጥ የተደጋገመ፣ ግን ደግሞ ያልተስተዋለ እውነት ነው።
ሄላም የወታደር ልጅ ናት፤ እንዲያሳድጋት በአደራ የተሰጠው ቤተሰብ የሚበድላት። የሷ ዓይነት ዕጣ ከደረሰው እንደ ወንድሟ ከምታየው ቴዲ ከሚባል ልጅ ጋር ታድጋለች። መጀመሪያ የሚልዮን፣ የኋላ ኋላ የምናሴ ፍቅረኛ የምትኾን ድምፀ-መረዋ ሴት ናት። ሁሉ ነገሯን ባጣችበት ወቅት ጡቷ ተአምር ያመርታል።
በመዝሙረ ሄላም ላይ የሄላም የጡት ወተት የአንዳች ነገር ውክል ይመስለኛል። ሻዕቢያ ለታጋይ ወጣቶች ማሳደጊያ ፈልጓት ሊሰርቃት መፈለጉ በቀላሉ የሚዘለል ነገር ነው? ወተት እና ጡት በመጀመሪያ እይታ የሕፃናት ትዝታ፣ የእናትነት ምሥል፣ የእምነት እና የጾታ መነሳሳት የተዋሃዱበትም አይደል? ወተት ሕይወት ነው? የመጀመሪያ ምግብ፣ ከእናት ወደ ልጅ የሚፈስም አይደል? በክርስቲያናዊ ምልክት ንጹሕነትን አይወክልም? ወተት ከ“ቅዱስ” ወደ “ሥጋዊ” የሚያስተላልፍ ድልድይ ነው ማለት እንችል ይኾን? የሄላምን ጡት የጠባ ታማሚ ልጅ እንዴት ጤናማ ሊኾን ቻለ? የምን ትእምርት ነው? ሄላም ከብዙ ወንድ ጋር የወጣች እንደመኾኗ ለዚህ ሰናይ ግብር ለምን የሷ ጡት ተመረጠ?
ሌላው፣ መዝሙረ ሄላም ላይ ኦልቬቲን እናገኛታለን። ኦልቬቲ የግራጫ ቃጭልዋ። መዝገቡ ንፋስ መውጫ ሳለ፣ ባልንጀራው ኤልያስ የብልግና ሀሁ ሊያስተምረው እፊቱ ያቆማት ቀይ ሰሌዳ ነበረች ኦልቬቲ። መዝሙረ ሄላም ላይ ምናሴን እና ቤተሰቡን የምታሾር ዐውራ ገጸባሕርይ ኾና ትከሰታለች። መዝሙረ ሄላም እና ግራጫ ቃጭሎች በጋለሞታይቱ በኦልቬቲ ብቻ ሳይኾን በዘመነ እንድርያስ እና በመዝገቡ ዱባለም ይገናኛሉ። ነጋ ዳቦ ጋጋሪውም በ-typological space መዝሙረ ሄላም ላይ እናገኘዋለን።
መዝሙረ ሄላምን ከህላዌነት (Existentialism) አንጻር እንመልከተው። ሄላም ትርጉም በማይሰጥ ዓለም ውስጥ እንዴት እንደምትኖር እናነባለን። የሀገሯ ዳር ድንበር እንዳይነካ አባት ብታዋጣም አሳዳጊዎቿ ግን የወላጅን ፍቅር አዋጥተው አይለግሷትም። ወርቅ አበድራ ጠጠር ትነፈጋለች። ዕቃ ለማገዝ ቤቷ ድረስ ለመጣው ሚልዮን ልቧን ትሰጣለች። ሀና የሸነቆረችውን ክፍተት ለሞላችበት ውለታዋ ክፍያ ይኾን ዘንድ ሚልዮን ለሄላም የወለፈንዴ ቡጢ ያሳርፍባታል። ለሕይወት ትርጉም ለመስጠት ባስ ውስጥ ካገኘችው ሄኖክ ጋር ብትሞክርም የበለጠ የሕይወት ትርጉም ይዛባባታል። የወታደር ልጅ መኾኗ ሄላምነቷን በዜሮ ያባዘዋል። የመጨረሻው ስንብትም ከሄኖክ ጓደኛ አፎት በሚወጣ ሰይፍ መቀላት ይኾናል። ከሄኖክ ጓደኛ ጀርባ የሚውለበለበው ባንዲራ ደግሞ የሄኖክ ሸሚዝ መኾኑ ደግሞ ቁስሉን እንደ አቡሰዲቅ ያደርገዋል። ለሕይወቷ ትልቅ ትርጉም ያለውን የሙዚቃ ሥራዋን፣ “ትርጉም ወዳለው
ነገር ይቀይርልኛል” ብላ በምትተማመንበት በምናሴ ትነጠቃለች። ተአምር በሚያስብለው በጡት ወተት ምክንያት ለሕይወቷ ትርጉም ለመስጠት ትታትራለች። የጡት ወተቷን ምርምር በማድረግ ለትልቅ ዓለምአቀፍ በጎ ተፅዕኖ ታደርጋለች ተብላ የተቆጠረችው ሥዕለማርያም የዓለም አቀፍ መሳለቂያና ትችት ምንጭ ትኾንባታለች። ይህ ሁሉ ትርጉም የሌለው ድግግሞሽ ነው። ይህ ደግሞ በሳርተር የተገለጸውን “existence without essence”-ን ያሳያል።
የህላዌነት መሠረታዊ ሐሳብ ነጻነት ነው፤ ግን ነጻነት ፍርሃትን ይወልዳል። ሄላም ለአሮን ፍቅሯን መናገር ትችላለች፤ ነገር ግን ዝምታን መርጣለች። የግራጫው መዝገቡ፣ የእንጀራ እናቱ የምታደርስበትን በደል እንደሚያውቀው ሁሉ ሄላምም ክብካብና ዘበናይ የሚያደርሱባትን አድሎ ታውቃለች፤ ግን ለረዥም ጊዜ ዝም ብላለች። ሄላም፣ ሙዚቃዋን ካጣች በኋላ ወደ ባንዱ ሄዳ መጋፈጥ ትችላለች፤ ነገር ግን አትሄድም … ይህ በሳርተርኛ bad faith ነው።
የሄላም ምርጫ ዝምታ ኾነ እንጂ ደካማ ናት ማለት አይደለም። “አልተናገርኩም ማለት አላውቀውም ማለት አይደለም” የሚል ዝምታ ነው ያላት። በሌላ ጎኑ ደግሞ ዝምታዋ፣ የለመደችውን ግፍ ከማታውቀው ዐዲስ ግፍ የመምረጥ ኹኔታ ነው። ዐዳዲስ ግፎችን ለመሸሽ በዝምታ አላዋቂነት ዛጎል ውስጥ የመደበቅ ብቃት ነው። የለመደችውን ግፍ የመከላከል አቅም ስላላት ባለመደችው ግፍ እንዳያጠፏት ሠግታ በውስጣዊ ንቃተ ሕሊና የዘየደችው ብልሃት ሊኾን ይችላል። ዝምታዋ የመቆየቷ ምሥጢር ነው። ደበበ ቀዝቃዛ ገለልተኛ ነኝ የሚለው ሰው ለመኖር ሲል ሳይታወቀው ስሜቱን የሚቆጣጠርበት መንገድን ለማስታወስ ነው።
“የስንብት ቀለማት” ገጸባሕርይ የኾነው ዮሴፍም ብዙ ነገር ያውቃል፤ ግን ዝም ይላል … ፊያሜታ ቂል መስሏት ትዘባርቃለች … እሱ ግን “አልተናገርኩም ማለት አላውቀውም ማለት አይደለም” የሚል የዝምታ መልስ ይመልስላታል። እሷ ግን ዝምታው አይገባትም። የ“ቀዳዳ”ው ደበበ እና “የስንብት …” ዮሴፍ ቀዳዳውን አይሞሉትም፤ እያዩት ይኖራሉ። ዶነሮች ጥሩ ፈንድ ሲለቁ ፊያሜታ ፕሮጀክቱን ለአሳምነው ትሰጠውና ዮሴፍን “ምን ዶነሮች እኮ ጠፉ ትለዋለች” … ዝም ይላል፤ ይታዘባል።
ቃል መሣሪያ ነበር፤ በዘመነ ደበበ፣ በዘመነ ዮሴፍ፣ በዘመነ ሄላም እና በዘመነ መዝገቡ ዱባለ ግን ቃል አደገኛ ኾኗል፤ ዝምታ ኹነኛ መጠጊያ ነው … ይህ ከደርግ በኋላ የተፈጠረ “traumatized literary silence” ማሳያ ነው። ስለኾነም ተራኪዎቹ (ደበበ፣ መዝገቡ፣ ዮሴፍ እና ሄላም) ለምን ዝም አሉ ሳይኾን "ዝምታን የሚያመነጭ ሥርዓት ምን ይኾን?" ብለን እንድንጠይቅ ያደርጋል። ግለሰብ ዝም ሲል፤ ሕዝብ በጸጥታ ይዋጣል፤ የዚያኔ የተማከለው ኃይል አፍ ያወጣል።
የአዳምን ዐዲሱን መጽሐፍ "በንባብ ይለቅ" ብለን መርቀናል።
ቢኒያም አቡራ
ሐምሌ 25 / 2018 ዓ.ም
14 hours ago
ግብር በቴሌብር ይቻላል!
ሰነድ ማዘጋጀትና ሰልፍ መሰለፍ ቀረ፤ የዓመቱን ግብር በቴሌብር አሁኑኑ እንክፈል!
ያለምንም መጉላላት፤ ከሥራ ገበታዎ ላይ ሳይነሱ በቴሌብር ባሉበት ሆነው ዓመታዊ ግብርዎን በቀላሉ ይክፈሉ!
ቴሌብር - እጅግ ቀላል፣ ፈጣን፣ ምቹ እና አስተማማኝ!
ቴሌብር ሱፐርአፕን https://bit.ly/telebirr_Su... ጭነን ስንከፍል እንዲህ ነን!
#ደንበኛ_ስንሆን_እንዲህ_ነን #ስንመዘገብ_እንዲህ_ነን #ስንጭን_እንዲህ_ነን #ስናስጀምር_እንዲህ_ነን
ሰነድ ማዘጋጀትና ሰልፍ መሰለፍ ቀረ፤ የዓመቱን ግብር በቴሌብር አሁኑኑ እንክፈል!
ያለምንም መጉላላት፤ ከሥራ ገበታዎ ላይ ሳይነሱ በቴሌብር ባሉበት ሆነው ዓመታዊ ግብርዎን በቀላሉ ይክፈሉ!
ቴሌብር - እጅግ ቀላል፣ ፈጣን፣ ምቹ እና አስተማማኝ!
ቴሌብር ሱፐርአፕን https://bit.ly/telebirr_Su... ጭነን ስንከፍል እንዲህ ነን!
#ደንበኛ_ስንሆን_እንዲህ_ነን #ስንመዘገብ_እንዲህ_ነን #ስንጭን_እንዲህ_ነን #ስናስጀምር_እንዲህ_ነን
15 hours ago
የፈረሰውን የአማኑኤልን ቤት አብረን እንሥራ!
(የደሀና ቅዱስ አማኑኤል ቤተክርስቲያን የማደስና የዕርዳታ ጥሪ)
የጥሪው ጭብጥ
ለብዙ ዘመናት የእግዚአብሔር ቃል ሲነገርበትና ምእመናን ሲገለገሉበት የቆየው የደሀና ቅዱስ አማኑኤል ቤተክርስቲያን መቅደስ በአሁኑ ወቅት በመፍረሱ ምክንያት ታሪካዊውና ቅዱሱ ቦታ የምስጥና የሸረሪት መኖሪያ ለመሆን በቅቷል።
የአካባቢው አባቶችና ምእመናን የፈረሰውን የእግዚአብሔር ቤት እንደገና ለመሥራት፦
«የአማኑኤል ወዳጆች የት አላችሁ? እጃችሁን ዘርጉልን፤ የፈረሰውን ቤቱን አብረን እንሥራ!» በማለት አጣዳፊ የድረሱልን ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።
እንዴት መደገፍ ይቻላል?
ኦርቶዶክሳውያን በሙሉ እንደየአቅማችን፦
በገንዘብ እርዳታ፦ ከ200 ብር ጀምሮ አነሰ፤ በዛ ሳንል ካለን ላይ በማካፈል፣
በአስራትና በበኩራት፦ የገጠሪቷን ቤተክርስቲያን በማሰብና በመደገፍ የበረከቱ ተካፋይ መሆን እንችላለን።
የባንክ ሂሳብ ቁጥር
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ (CBE): 1000781694588
የሂሳብ ስም: የደሀና ቅዱስ አማኑኤል ቤተክርስቲያን
ለበለጠ መረጃ እና ለጸሎት
ስልክ ቁጥር: 0941929014
(እርዳታ ያደረጋችሁ ምእመናን የክርስትና ስማችሁን በቴሌግራም ወይም በዋትስአፕ በዚሁ ስልክ ቁጥር በመላክ በኪዳን፣ በሰዓታት፣ በቅዳሴና በጸሎት አባቶች እንዲያስቡአችሁ ማድረግ ትችላላችሁ።)
መልእክቱን ሼር (Share) በማድረግ የጽድቁ ተካፋይ ይሁኑ!
1 day ago
ተንቀሳቃሽ ቤተ-መጽሐፍት፡ ስልክ ላይ የማቀርቀርን አዚም የሰበረው ባለታክሲ
********************
በአዲስ አበባ ጎዳናዎች ላይ የሚንቀሳቀሱ የሕዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጡ ታክሲዎች አብዛኛውን ጊዜ በሙዚቃ ጩኸት፣ በትራፊክ ጫጫታና በጉዞ ድካም አዙሪት ውስጥ በመቆየት ይታወቃሉ።
ተሳፋሪውም ታክሲ ውስጥ እንደገባ አንገቱን ደፍቶ በማህበራዊ ሚዲያ ገጾች ላይ መንሸራሸር የዘመናችን የተለመደ እውነታ ሆኗል። ወጣት ሰሎሞን አማረ ግን፣ የራሱን ሜትር ታክሲ ከዚህ አሰልቺ እና የተለመደ ምህዋር በማውጣት በአዲስ አበባ ጎዳናዎች ላይ ወደ የሚሽከረከር "ተንቀሳቃሽ ቤተ-መጽሐፍት" ቀይሮታል።
በንግድና በጥድፊያ በሚታወቀው የመርካቶ ሰባተኛ ሰፈር ተወልዶ ያደገው ሰሎሞን፣ ከቅድስተ ማርያም ዩኒቨርሲቲ በማርኬቲንግ ማኔጅመንት የመጀመሪያ ዲግሪውን አግኝቷል። ከዲጂታል ሚዲያው መስፋፋት ጋር ተያይዞ ህብረተሰቡ፣ በተለይም ወጣቱ፣ ከመጽሐፍት እየራቀ መምጣቱ በእጅጉ አሳስቦታል። በዚህም የተነሳ፣ ላለፉት ጥቂት ወራት ታክሲውን የዕውቀት ማዕከል በማድረግ ልዩ ልዩ የአማርኛና የእንግሊዝኛ መጻሕፍትን ለተሳፋሪዎቹ እንደ አዲስ አማራጭ ማቅረብ ጀምሯል።
ሁሉም ሰው ስልኩ ላይ ባቀረቀረበት በዚህ ዘመን፣ ሰሎሞን የታክሲው ውስጥ መደርደሪያዎች ላይ መጽሐፍትን በማስቀመጥ የሰዎችን ትኩረት ወደ ንባብ ለመመለስ የራሱን የትግል ስልት ነድፏል።
ሰለሞን ወደ ታክሲው ለሚገቡ መንገደኞች የሚያቀርበው ሞቅ ያለ ፈገግታና ሰላምታን ብቻ አይደለም፤ በስርዓት የተደረደሩ የዕውቀት ማህደሮችንም ጭምር እንጂ። የትራፊክ መጨናነቅን እንደ መልካም አጋጣሚ በመጠቀም፣ ተሳፋሪዎች በጉዞ ወቅት መጽሐፍትን እንዲያነቡ ይጋብዛል።
የጀመሩት መጽሐፍ ልባቸውን ከሰረቀው ደግሞ፣ እዚያው ታክሲ ውስጥ ገዝተውት መንገዳቸውን ያለመሰልቸት በዕውቀት ታጅበው ያጠናቅቃሉ። ይህ አሰራር ከማህበራዊ ሚዲያ ጩኸት ለተወሰኑ ደቂቃዎችም ቢሆን አእምሮን የሚያሳርፉበት ልዩ የጉዞ ተሞክሮ ሆኗል።
የሰሎሞን አካሄድ የንባብ ባህልን ከማበረታታት ባለፈ፣ የገበያ ጥናትን (Marketing Management) ከተግባር ጋር ያዋሃደ አዲስ የስራ ፈጠራ ነው።
ጊዜን ወደ እሴት መቀየር፡ የታክሲ ተሳፋሪን የትራፊክ ውስጥ የባከነ ጊዜ ወደ ምርታማ የገበያ ሰዓት ቀይሮታል።
ድርብ ገቢ፡ ከትራንስፖርት አገልግሎቱ ባሻገር፣ መጽሐፍትን በመሸጥ የራሱን የገቢ ምንጭ አሳድጓል።
ማህበራዊ ካፒታል፡ "ተሳፋሪዎች የሚሰጡት አዎንታዊ ምላሽና አስደናቂ ስሜት ለስራዬ ትልቅ መነቃቃት ይፈጥርልኛል" የሚለው ሰሎሞን፣ በየቀኑ ከሚያገኛቸው አዳዲስ ሰዎች ጋር የሚያደርገው ገንቢ ውይይት ከገንዘብ በላይ የሆነ ትልቅ የህይወት ስንቅ እንደሆነለት ይናገራል።
የሰሎሞን አስገራሚው ጎን የዲጂታል ዓለሙን ሙሉ በሙሉ መሸሹ ሳይሆን፣ ቴክኖሎጂውን ለራሱ ዓላማ ማዋሉ ነው። "Sol Books" በሚል ስያሜ በቲክቶክና በሌሎች ማኅበራዊ ገጾች መጻሕፍትን በማስተዋወቅ፣ ዲጂታል ትውልዱን በዲጂታል መድረክ እየቀሰቀሰ ይገኛል።
የዚህ አብዮተኛ ወጣት መልዕክት አጭር እና ግልጽ ነው፦ የተለመደውን አሰራር በመስበር ሌሎች የትራንስፖርት አገልግሎት ሰጪዎችም ይህን መሰል በጎ ተግባር ቢያራምዱ፣ ታክሲዎቻችንን ከትራፊክ ጫና ማምለጫነት አልፈው የዕውቀት፣ የሰላምና የፈጠራ ማዕከል ማድረግ ይቻላል።
በሊያ ተስፋዬ
Ethiopian Broadcasting Corporation FM Addis 97.1 /ኤፍ ኤም አዲስ 97.1 ሬዲዮ/ #መጽሀፍ #ንባብ
********************
በአዲስ አበባ ጎዳናዎች ላይ የሚንቀሳቀሱ የሕዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጡ ታክሲዎች አብዛኛውን ጊዜ በሙዚቃ ጩኸት፣ በትራፊክ ጫጫታና በጉዞ ድካም አዙሪት ውስጥ በመቆየት ይታወቃሉ።
ተሳፋሪውም ታክሲ ውስጥ እንደገባ አንገቱን ደፍቶ በማህበራዊ ሚዲያ ገጾች ላይ መንሸራሸር የዘመናችን የተለመደ እውነታ ሆኗል። ወጣት ሰሎሞን አማረ ግን፣ የራሱን ሜትር ታክሲ ከዚህ አሰልቺ እና የተለመደ ምህዋር በማውጣት በአዲስ አበባ ጎዳናዎች ላይ ወደ የሚሽከረከር "ተንቀሳቃሽ ቤተ-መጽሐፍት" ቀይሮታል።
በንግድና በጥድፊያ በሚታወቀው የመርካቶ ሰባተኛ ሰፈር ተወልዶ ያደገው ሰሎሞን፣ ከቅድስተ ማርያም ዩኒቨርሲቲ በማርኬቲንግ ማኔጅመንት የመጀመሪያ ዲግሪውን አግኝቷል። ከዲጂታል ሚዲያው መስፋፋት ጋር ተያይዞ ህብረተሰቡ፣ በተለይም ወጣቱ፣ ከመጽሐፍት እየራቀ መምጣቱ በእጅጉ አሳስቦታል። በዚህም የተነሳ፣ ላለፉት ጥቂት ወራት ታክሲውን የዕውቀት ማዕከል በማድረግ ልዩ ልዩ የአማርኛና የእንግሊዝኛ መጻሕፍትን ለተሳፋሪዎቹ እንደ አዲስ አማራጭ ማቅረብ ጀምሯል።
ሁሉም ሰው ስልኩ ላይ ባቀረቀረበት በዚህ ዘመን፣ ሰሎሞን የታክሲው ውስጥ መደርደሪያዎች ላይ መጽሐፍትን በማስቀመጥ የሰዎችን ትኩረት ወደ ንባብ ለመመለስ የራሱን የትግል ስልት ነድፏል።
ሰለሞን ወደ ታክሲው ለሚገቡ መንገደኞች የሚያቀርበው ሞቅ ያለ ፈገግታና ሰላምታን ብቻ አይደለም፤ በስርዓት የተደረደሩ የዕውቀት ማህደሮችንም ጭምር እንጂ። የትራፊክ መጨናነቅን እንደ መልካም አጋጣሚ በመጠቀም፣ ተሳፋሪዎች በጉዞ ወቅት መጽሐፍትን እንዲያነቡ ይጋብዛል።
የጀመሩት መጽሐፍ ልባቸውን ከሰረቀው ደግሞ፣ እዚያው ታክሲ ውስጥ ገዝተውት መንገዳቸውን ያለመሰልቸት በዕውቀት ታጅበው ያጠናቅቃሉ። ይህ አሰራር ከማህበራዊ ሚዲያ ጩኸት ለተወሰኑ ደቂቃዎችም ቢሆን አእምሮን የሚያሳርፉበት ልዩ የጉዞ ተሞክሮ ሆኗል።
የሰሎሞን አካሄድ የንባብ ባህልን ከማበረታታት ባለፈ፣ የገበያ ጥናትን (Marketing Management) ከተግባር ጋር ያዋሃደ አዲስ የስራ ፈጠራ ነው።
ጊዜን ወደ እሴት መቀየር፡ የታክሲ ተሳፋሪን የትራፊክ ውስጥ የባከነ ጊዜ ወደ ምርታማ የገበያ ሰዓት ቀይሮታል።
ድርብ ገቢ፡ ከትራንስፖርት አገልግሎቱ ባሻገር፣ መጽሐፍትን በመሸጥ የራሱን የገቢ ምንጭ አሳድጓል።
ማህበራዊ ካፒታል፡ "ተሳፋሪዎች የሚሰጡት አዎንታዊ ምላሽና አስደናቂ ስሜት ለስራዬ ትልቅ መነቃቃት ይፈጥርልኛል" የሚለው ሰሎሞን፣ በየቀኑ ከሚያገኛቸው አዳዲስ ሰዎች ጋር የሚያደርገው ገንቢ ውይይት ከገንዘብ በላይ የሆነ ትልቅ የህይወት ስንቅ እንደሆነለት ይናገራል።
የሰሎሞን አስገራሚው ጎን የዲጂታል ዓለሙን ሙሉ በሙሉ መሸሹ ሳይሆን፣ ቴክኖሎጂውን ለራሱ ዓላማ ማዋሉ ነው። "Sol Books" በሚል ስያሜ በቲክቶክና በሌሎች ማኅበራዊ ገጾች መጻሕፍትን በማስተዋወቅ፣ ዲጂታል ትውልዱን በዲጂታል መድረክ እየቀሰቀሰ ይገኛል።
የዚህ አብዮተኛ ወጣት መልዕክት አጭር እና ግልጽ ነው፦ የተለመደውን አሰራር በመስበር ሌሎች የትራንስፖርት አገልግሎት ሰጪዎችም ይህን መሰል በጎ ተግባር ቢያራምዱ፣ ታክሲዎቻችንን ከትራፊክ ጫና ማምለጫነት አልፈው የዕውቀት፣ የሰላምና የፈጠራ ማዕከል ማድረግ ይቻላል።
በሊያ ተስፋዬ
Ethiopian Broadcasting Corporation FM Addis 97.1 /ኤፍ ኤም አዲስ 97.1 ሬዲዮ/ #መጽሀፍ #ንባብ
Sponsored by
Surafel
2 days ago
የዘመናችን ሉዓላዊነት፡ ከድንበር ጥበቃ እስከ ኢኮኖሚያዊና ዲጂታል ልዕልና
*******************
( የዕለቱ መልዕክት)
ትናንት የሀገር ዳር ድንበር በጀግኖች ደምና አጥንት ይጠበቅ ነበር። ዛሬ ግን የዓለማችን የጂኦ-ፖለቲካ መልክ እና የኃይል አሰላለፍ መሰረታዊ ለውጥ ሲያስተናግድ፣ የሉዓላዊነት ትርጓሜም እጅግ ጥልቅ የሆነ አዲስ ገጽታን ተላብሷል።
በ21ኛው ክፍለ ዘመን የኢትዮጵያ ሉዓላዊነት እና የህልውና ዋስትና የሚረጋገጠው ጂኦግራፊያዊ ድንበርን በጦር መሣሪያ በመጠበቅ ብቻ ሳይሆን በስንዴ ማሳዎቻችን ስፋት፣ በፋብሪካዎቻችን የማምረት አቅም እንዲሁም በዲጂታል ቴክኖሎጂ ብቃታችን ጭምር ነው።
እውነተኛ ነፃነት ማለት የራስን ትርክት በራስ አቅም መጻፍ መቻል፣ የራስን ህዝብ በራስ አቅም መመገብ እና የሀገርን ጉዳይ ያለ አንዳች የውጭ ጫና መወሰን መቻል ማለት ነው።
ይህ ሉዓለዊነት ከእርዳታ ጥገኝነት እና ከተረጂነት አዘቅት ተላቆ በምግብ ራስን መቻልን፣ ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ አቅም ማምረትን እና በከንቱ የሚባክኑ የተፈጥሮ ጸጋዎቻችንን ወደ ሀገራዊ ሀብት መቀየርን ማዕከል ያደረገ ነው።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) "ደሃ አይከበርም፤ እየለመነ የሚኖር ሀገር አይከበርም" ሲሉ የተናገሩት መራር ሀቅ፣ የዘመናችንን የሉዓላዊነት ትግል ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ ነው። ክብራችን በዓለም አቀፍ መድረክ ላይ ደምቆ የሚታየው፣ ቃላችንም የሚሰማው ፖሊሲዎቻችንን ያለማንም ጣልቃ ገብነት ማስፈጸም የሚያስችል የኢኮኖሚ ጡንቻ ስንገነባ ብቻ መሆኑን ይህ አዲስ እሳቤ ያስገነዝበናል።
ይህ ሁለንተናዊ የኢኮኖሚ እና የቴክኖሎጂ ሉዓላዊነት እርስበርስ በተሳሰሩ ጠንካራ ምሰሶዎች ላይ የቆመ ነው። የግብርናው ዘርፍ ዜጎችን ከረሃብ ከመታደግ አልፎ፣ ሀገርን በእርዳታ ስም ከሚመጣ የፖለቲካ ተጽዕኖ እና የውጭ ጫና ነጻ የማውጣት አቅም አለው።
ከዚህ ጎን ለጎን አምራች ኢንዱስትሪውና ማዕድን ልማቱ የውጭ ምንዛሬን በማስገኘት ሀገራዊ ሜጋ ፕሮጀክቶቻችንን በራሳችን አቅም እንድንገነባና ኢኮኖሚያችን እንዲጠናከሩ እያደረጉ ይገኛሉ። የቱሪዝም ዘርፉ የብሔራዊ ገጽታችንን ከመገንባት ባሻገር ባህላችንን ለዓለም የምናስተዋውቅበት የሶፍት ፓወር መሣሪያችን ሲሆን የዲጂታል ኢኮኖሚው ደግሞ ከዘመኑ የቴክኖሎጂ ፍጥነት ጋር እኩል እንድንራመድ የሚያደርገን የህልውናችን ወሳኝ ቁልፍ ሆኗል።
የታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ የሉኣላዊነታችን መከበር ትልቁ ማሳያ ነው። ዓለም አቀፍ ጫናዎችን ተቋቁመን ግድቡን ከዳር ማድረሳችን፣ ወደ ብሪክስ (BRICS) አባልነት መቀላቀላችን እና የባህር በር ጥያቄያችንን በዲፕሎማሲያዊ መንገድ ለማሳካት የምናደርገው ትጋት ሀገራችን በዓለም አቀፍ መድረክ ያላትን ተሰሚነት እና ሉዓላዊ ክብሯን በተጨባጭ የሚያሳዩም ናቸው።
ይሁን እንጂ፣ እነዚህ ታላላቅ ሀገራዊ ስኬቶችና የዲፕሎማሲ ድሎች ዘላቂና ሙሉ ትርጉም የሚኖራቸው በውስጣችን ሰላምና ሀገራዊ መግባባት ሲሰፍን ብቻ መሆኑን መዘንጋት የለብንም። የልዩነት ግንቦችን አፍርሰን በጠረጴዛ ዙሪያ በሀገራዊ ምክክር ካልተወያየን እንዲሁም የጋራ ጠላታችን በሆነው ድህነት ላይ በአንድነት ካልዘመትን፣ የጀመርነውን የብልጽግና ጉዞ ማሳካትና ሉዓላዊነታችንን ከውስጥም ከውጭም ማስጠበቅ እጅግ ይከብዳል። የኢኮኖሚና የዲጂታል ልዕልናን ለማረጋገጥ መነሻው የውስጥ ሰላምና የአንድነት መንፈስ ነው።
በሌላ በኩል ደግሞ ይህን ሁለንተናዊ የልማት ጉዞ እውን ለማድረግ የሀገርን ሉዓላዊነት እና የሕዝባችንን ሰላም ለማስጠበቅ ሌሊትና ቀን የሚተጋው፣ በቆራጥነትና በጀግንነት የተገነባው መከላከያ ሠራዊታችን ሚና በጉልህ የሚጠቀስ ነዉ፡፡
ሠራዊቱ ለሀገሩና ለህዝቡ ሲል ዛሬም ይፋለማል፣ ይዋደቃል፣ የተከበረ ህይወቱንም ይሰጣል። ይህ ሠራዊት ሀገሩን ከውጭና ከውስጥ ፀረ-ሰላም ኃይሎች በመጠበቅ የሉዓላዊነታችን ጠንካራ ዘብ በመሆን ለልማታችን ምቹ ሁኔታን ይፈጥራል።
የሠራዊቱን የጀግንነት ፈለግ በመከተል ሕዝብ በአንድነት ሲቆም፣ አገርን ከጠላት መጠበቅና ወደ ብልጽግና ማሻገር ይቻላል። ስለዚህም የሀገርን ድንበርና ሰላም በንቃት መጠበቅ እንዲሁም ለጸጥታ አካላት ጠንካራ ድጋፍና አጋርነት ማሳየት የሁሉም ዜጋ ግዴታ ነው።
ስለሆነም አሁን ጊዜው ታሪካዊ ጀግንነታችንን ወደ አዲስ ምዕራፍ የምናሸጋግርበት ወቅት ነው። ሀገራዊ ሉዓላዊነታችንን ዘላቂ ለማድረግ፣ ሁለንተናዊ ብልጽግናችንን ለማረጋገጥ እንዲሁም ትግላችንን ከጦር ሜዳ ወደ ዲጂታል ፈጠራ፣ ከተረጂነት ወደ አምራችነት እና ወደ ጠንካራ የስራ ባህል የምናሸጋግርበት ወሳኝ የለውጥ ዘመን ላይ እንገኛለን። የትናንት አባቶቻችን በደማቸው ያቆዩልንን ነጻነት፣ ዛሬ በላባችን፣ በእውቀታችን እና በፈጠራ ክህሎታችን ልናደምቀው ግድ ይለናል!
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
*******************
( የዕለቱ መልዕክት)
ትናንት የሀገር ዳር ድንበር በጀግኖች ደምና አጥንት ይጠበቅ ነበር። ዛሬ ግን የዓለማችን የጂኦ-ፖለቲካ መልክ እና የኃይል አሰላለፍ መሰረታዊ ለውጥ ሲያስተናግድ፣ የሉዓላዊነት ትርጓሜም እጅግ ጥልቅ የሆነ አዲስ ገጽታን ተላብሷል።
በ21ኛው ክፍለ ዘመን የኢትዮጵያ ሉዓላዊነት እና የህልውና ዋስትና የሚረጋገጠው ጂኦግራፊያዊ ድንበርን በጦር መሣሪያ በመጠበቅ ብቻ ሳይሆን በስንዴ ማሳዎቻችን ስፋት፣ በፋብሪካዎቻችን የማምረት አቅም እንዲሁም በዲጂታል ቴክኖሎጂ ብቃታችን ጭምር ነው።
እውነተኛ ነፃነት ማለት የራስን ትርክት በራስ አቅም መጻፍ መቻል፣ የራስን ህዝብ በራስ አቅም መመገብ እና የሀገርን ጉዳይ ያለ አንዳች የውጭ ጫና መወሰን መቻል ማለት ነው።
ይህ ሉዓለዊነት ከእርዳታ ጥገኝነት እና ከተረጂነት አዘቅት ተላቆ በምግብ ራስን መቻልን፣ ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ አቅም ማምረትን እና በከንቱ የሚባክኑ የተፈጥሮ ጸጋዎቻችንን ወደ ሀገራዊ ሀብት መቀየርን ማዕከል ያደረገ ነው።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) "ደሃ አይከበርም፤ እየለመነ የሚኖር ሀገር አይከበርም" ሲሉ የተናገሩት መራር ሀቅ፣ የዘመናችንን የሉዓላዊነት ትግል ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ ነው። ክብራችን በዓለም አቀፍ መድረክ ላይ ደምቆ የሚታየው፣ ቃላችንም የሚሰማው ፖሊሲዎቻችንን ያለማንም ጣልቃ ገብነት ማስፈጸም የሚያስችል የኢኮኖሚ ጡንቻ ስንገነባ ብቻ መሆኑን ይህ አዲስ እሳቤ ያስገነዝበናል።
ይህ ሁለንተናዊ የኢኮኖሚ እና የቴክኖሎጂ ሉዓላዊነት እርስበርስ በተሳሰሩ ጠንካራ ምሰሶዎች ላይ የቆመ ነው። የግብርናው ዘርፍ ዜጎችን ከረሃብ ከመታደግ አልፎ፣ ሀገርን በእርዳታ ስም ከሚመጣ የፖለቲካ ተጽዕኖ እና የውጭ ጫና ነጻ የማውጣት አቅም አለው።
ከዚህ ጎን ለጎን አምራች ኢንዱስትሪውና ማዕድን ልማቱ የውጭ ምንዛሬን በማስገኘት ሀገራዊ ሜጋ ፕሮጀክቶቻችንን በራሳችን አቅም እንድንገነባና ኢኮኖሚያችን እንዲጠናከሩ እያደረጉ ይገኛሉ። የቱሪዝም ዘርፉ የብሔራዊ ገጽታችንን ከመገንባት ባሻገር ባህላችንን ለዓለም የምናስተዋውቅበት የሶፍት ፓወር መሣሪያችን ሲሆን የዲጂታል ኢኮኖሚው ደግሞ ከዘመኑ የቴክኖሎጂ ፍጥነት ጋር እኩል እንድንራመድ የሚያደርገን የህልውናችን ወሳኝ ቁልፍ ሆኗል።
የታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ የሉኣላዊነታችን መከበር ትልቁ ማሳያ ነው። ዓለም አቀፍ ጫናዎችን ተቋቁመን ግድቡን ከዳር ማድረሳችን፣ ወደ ብሪክስ (BRICS) አባልነት መቀላቀላችን እና የባህር በር ጥያቄያችንን በዲፕሎማሲያዊ መንገድ ለማሳካት የምናደርገው ትጋት ሀገራችን በዓለም አቀፍ መድረክ ያላትን ተሰሚነት እና ሉዓላዊ ክብሯን በተጨባጭ የሚያሳዩም ናቸው።
ይሁን እንጂ፣ እነዚህ ታላላቅ ሀገራዊ ስኬቶችና የዲፕሎማሲ ድሎች ዘላቂና ሙሉ ትርጉም የሚኖራቸው በውስጣችን ሰላምና ሀገራዊ መግባባት ሲሰፍን ብቻ መሆኑን መዘንጋት የለብንም። የልዩነት ግንቦችን አፍርሰን በጠረጴዛ ዙሪያ በሀገራዊ ምክክር ካልተወያየን እንዲሁም የጋራ ጠላታችን በሆነው ድህነት ላይ በአንድነት ካልዘመትን፣ የጀመርነውን የብልጽግና ጉዞ ማሳካትና ሉዓላዊነታችንን ከውስጥም ከውጭም ማስጠበቅ እጅግ ይከብዳል። የኢኮኖሚና የዲጂታል ልዕልናን ለማረጋገጥ መነሻው የውስጥ ሰላምና የአንድነት መንፈስ ነው።
በሌላ በኩል ደግሞ ይህን ሁለንተናዊ የልማት ጉዞ እውን ለማድረግ የሀገርን ሉዓላዊነት እና የሕዝባችንን ሰላም ለማስጠበቅ ሌሊትና ቀን የሚተጋው፣ በቆራጥነትና በጀግንነት የተገነባው መከላከያ ሠራዊታችን ሚና በጉልህ የሚጠቀስ ነዉ፡፡
ሠራዊቱ ለሀገሩና ለህዝቡ ሲል ዛሬም ይፋለማል፣ ይዋደቃል፣ የተከበረ ህይወቱንም ይሰጣል። ይህ ሠራዊት ሀገሩን ከውጭና ከውስጥ ፀረ-ሰላም ኃይሎች በመጠበቅ የሉዓላዊነታችን ጠንካራ ዘብ በመሆን ለልማታችን ምቹ ሁኔታን ይፈጥራል።
የሠራዊቱን የጀግንነት ፈለግ በመከተል ሕዝብ በአንድነት ሲቆም፣ አገርን ከጠላት መጠበቅና ወደ ብልጽግና ማሻገር ይቻላል። ስለዚህም የሀገርን ድንበርና ሰላም በንቃት መጠበቅ እንዲሁም ለጸጥታ አካላት ጠንካራ ድጋፍና አጋርነት ማሳየት የሁሉም ዜጋ ግዴታ ነው።
ስለሆነም አሁን ጊዜው ታሪካዊ ጀግንነታችንን ወደ አዲስ ምዕራፍ የምናሸጋግርበት ወቅት ነው። ሀገራዊ ሉዓላዊነታችንን ዘላቂ ለማድረግ፣ ሁለንተናዊ ብልጽግናችንን ለማረጋገጥ እንዲሁም ትግላችንን ከጦር ሜዳ ወደ ዲጂታል ፈጠራ፣ ከተረጂነት ወደ አምራችነት እና ወደ ጠንካራ የስራ ባህል የምናሸጋግርበት ወሳኝ የለውጥ ዘመን ላይ እንገኛለን። የትናንት አባቶቻችን በደማቸው ያቆዩልንን ነጻነት፣ ዛሬ በላባችን፣ በእውቀታችን እና በፈጠራ ክህሎታችን ልናደምቀው ግድ ይለናል!
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
4 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና ዳሰሳ) የሶማሌላንድ የሀገርነት ጥያቄ እና አለም አቀፍ እውቅና የማግኘት ፍላጎት በዋናነት የተመሰረተው በቅኝ ግዛት ወቅት በነበራት ግልጽ ድንበር፣ እ.ኤ.አ. በ1960 ለተወሰኑ ቀናት አግኝታው በነበረው ነጻነት እና በ1991 ያወጀችው ነጻነት አዲስ የመገንጠል ጥያቄ ሳይሆን የነበረን ሉዓላዊነት የመመለስ እርምጃ ነው በሚለው መከራከሪያ ላይ ነው። እንግሊዝ ከ1884 እስከ 1886 በሰሜን ሶማሊያ ከሚገኙ የጎሳ መሪዎች ጋር ባደረገችው የስምምነት ውል መሰረት የሶማሌላንድን ግዛት የመሰረተች ሲሆን፣ የውጭ ድንበሮቿም ከፈረንሳይ፣ ጣሊያን እና ኢትዮጵያ ጋር በተደረጉ አለም አቀፍ ስምምነቶች የተከለሉ ነበሩ። ሰኔ 26 ቀን 1960 ከእንግሊዝ ቅኝ ግዛት ነጻነቷን የተቀዳጀችው ሶማሌላንድ፣ ከአምስት ቀናት በኋላ በፈቃደኝነት ከጣሊያን ሶማሊያ ጋር በመዋሃድ የሶማሊያ ሪፐብሊክን መስርታለች። ይሁን እንጂ የሶማሊያ ማዕከላዊ መንግስት በ1991 መውደቁን ተከትሎ፣ ሶማሌላንድ ከውህደቱ በፊት ወደ ነበራት ነጻነት መመለሷን በማወጅ የ1960ዋን ግዛቷን ይዛለች።
የሶማሌላንድ ዋነኛ የህግ መከራከሪያ አዲስ ነጻ የሚወጡ ሀገራት በቅኝ ግዛት ወቅት የነበራቸውን ድንበር ጠብቀው ሊቀጥሉ ይገባል የሚለው መርህ ነው። የአፍሪካ አንድነት ድርጅት በ1964ቱ የካይሮ ውሳኔው እንዲሁም የአፍሪካ ህብረት የመመስረቻ ሰነዱ ላይ አባል ሀገራት በነጻነት ጊዜ የነበራቸውን ድንበር ሊያከብሩ እንደሚገባ አስፍረዋል። በመሆኑም ሶማሌላንድ አለም አቀፍ እውቅና ማግኘቷ የቅኝ ግዛት ድንበርን ከመጠበቅ ባለፈ አዲስ ድንበር የማካለል ስራ አይደለም በማለት ትከራከራለች። አቋሟም ከዚህ ቀደም ሉዓላዊ ሀገር እንደነበረች፣ የ1960ውን ውህደት በራሷ ፈቃድ እንደፈጸመች እና የ1991ዱ እርምጃዋም የከሸፈን ውህደት ማፍረስ እንጂ አዲስ ግዛትን ከሶማሊያ መገንጠል አይደለም በሚሉ ሶስት ምሶሶዎች ላይ የቆመ ነው። ይህ አቀራረብ ሶማሌላንድን ምንም አይነት የቅኝ ግዛት ወይም አለም አቀፍ ድንበር መሰረት ከሌላቸው የመገንጠል ጥያቄዎች የተለየች ያደርጋታል።
የሶማሌላንድን ሁኔታ ከኤርትራ ጋር ማነጻጸር የጉዳዩን የዲፕሎማሲ ውስብስብነት በደንብ ያሳያል። ሁለቱም ግዛቶች የተለየ የቅኝ ግዛት ታሪክ፣ ከማዕከላዊ መንግስት ጋር የተደረገ የትጥቅ ትግል እና ከ1991 በኋላ ውጤታማ የሆነ ራስን በራስ የማስተዳደር ልምድ አላቸው። ይሁን እንጂ የኤርትራ የነጻነት ጥያቄ የኢትዮጵያን የሽግግር መንግስት ፈቃድ እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የህዝበ ውሳኔ ታዛቢነትን በማግኘቱ ፈጣን አለም አቀፍ እውቅናን ሊያጎናጽፋት ችሏል። በሶማሌላንድ በኩል ግን ጠንካራ ተቋማትን መገንባት እና ህዝበ ውሳኔ ማካሄድ ብትችልም፣ ከሶማሊያ መንግስት የተገኘ ስምምነትም ሆነ እንደ ኤርትራው አይነት አለም አቀፍ ድጋፍ ባለማግኘቷ የዲፕሎማሲ እውቅናው ሊዘገይባት ችሏል። ይህ የሚያሳየው ውጤታማ አስተዳደር እና ታሪካዊ ድንበር መኖር ብቻውን በቂ እንዳልሆነ እና እውቅና ማግኘት በስምምነት፣ በቀጠናዊ ፖለቲካ እና በዲፕሎማሲያዊ ድጋፍ ላይ በእጅጉ የተመሰረተ መሆኑን ነው።
የአፍሪካ ህብረት በ2005 ወደ አካባቢው አጣሪ ቡድን ልኮ የሶማሌላንድ ጥያቄ በቅኝ ግዛት ድንበር እና በቀድሞ ነጻነቷ ላይ የተመሰረተ ታሪካዊ መነሻ እንዳለው ቢገነዘብም፣ አሁንም ድረስ ለሶማሊያ ሉዓላዊነት እና የግዛት አንድነት ቅድሚያ መስጠትን መርጧል። በርካታ የአፍሪካ ሀገራት ሶማሌላንድን እውቅና መስጠት በሌሎች አካባቢዎች የመገንጠል ጥያቄዎችን ሊያነሳሳ ይችላል የሚል ስጋት አላቸው። ሶማሌላንድ በበኩሏ የድሮውን ድንበር መመለስ እንጂ አዲስ ድንበር መፍጠር አይደለም ስትል ምላሽ ትሰጣለች።
ሶማሌላንድ በቅኝ ግዛት ድንበር እና በቀድሞ ነጻነት ላይ የተመሰረተ ጠንካራ የህግ መከራከሪያ ብታቀርብም፣ የኤርትራን ተሞክሮ ስንመለከት የህግ ትንታኔ ብቻውን እውቅናን እንደማያመጣ መገንዘብ ይቻላል። ሶማሌላንድ ከሶማሊያ ጋር የደረሰችበት ምንም አይነት ስምምነት ባለመኖሩ፣ የእውቅና ጉዳይ አሁንም ድረስ አለም አቀፍ ተቋማት የድሮዋን ሉዓላዊ ሀገር ዳግም መመለስ አድርገው ይቀበሉታል ወይስ የሶማሊያን የግዛት አንድነት የሚፈታተን ድርጊት አድርገው ይቆጥሩታል የሚለው ጉዳይ የፈተና መድረክ ሆኖ ቀጥሏል።
የሶማሌላንድ ዋነኛ የህግ መከራከሪያ አዲስ ነጻ የሚወጡ ሀገራት በቅኝ ግዛት ወቅት የነበራቸውን ድንበር ጠብቀው ሊቀጥሉ ይገባል የሚለው መርህ ነው። የአፍሪካ አንድነት ድርጅት በ1964ቱ የካይሮ ውሳኔው እንዲሁም የአፍሪካ ህብረት የመመስረቻ ሰነዱ ላይ አባል ሀገራት በነጻነት ጊዜ የነበራቸውን ድንበር ሊያከብሩ እንደሚገባ አስፍረዋል። በመሆኑም ሶማሌላንድ አለም አቀፍ እውቅና ማግኘቷ የቅኝ ግዛት ድንበርን ከመጠበቅ ባለፈ አዲስ ድንበር የማካለል ስራ አይደለም በማለት ትከራከራለች። አቋሟም ከዚህ ቀደም ሉዓላዊ ሀገር እንደነበረች፣ የ1960ውን ውህደት በራሷ ፈቃድ እንደፈጸመች እና የ1991ዱ እርምጃዋም የከሸፈን ውህደት ማፍረስ እንጂ አዲስ ግዛትን ከሶማሊያ መገንጠል አይደለም በሚሉ ሶስት ምሶሶዎች ላይ የቆመ ነው። ይህ አቀራረብ ሶማሌላንድን ምንም አይነት የቅኝ ግዛት ወይም አለም አቀፍ ድንበር መሰረት ከሌላቸው የመገንጠል ጥያቄዎች የተለየች ያደርጋታል።
የሶማሌላንድን ሁኔታ ከኤርትራ ጋር ማነጻጸር የጉዳዩን የዲፕሎማሲ ውስብስብነት በደንብ ያሳያል። ሁለቱም ግዛቶች የተለየ የቅኝ ግዛት ታሪክ፣ ከማዕከላዊ መንግስት ጋር የተደረገ የትጥቅ ትግል እና ከ1991 በኋላ ውጤታማ የሆነ ራስን በራስ የማስተዳደር ልምድ አላቸው። ይሁን እንጂ የኤርትራ የነጻነት ጥያቄ የኢትዮጵያን የሽግግር መንግስት ፈቃድ እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የህዝበ ውሳኔ ታዛቢነትን በማግኘቱ ፈጣን አለም አቀፍ እውቅናን ሊያጎናጽፋት ችሏል። በሶማሌላንድ በኩል ግን ጠንካራ ተቋማትን መገንባት እና ህዝበ ውሳኔ ማካሄድ ብትችልም፣ ከሶማሊያ መንግስት የተገኘ ስምምነትም ሆነ እንደ ኤርትራው አይነት አለም አቀፍ ድጋፍ ባለማግኘቷ የዲፕሎማሲ እውቅናው ሊዘገይባት ችሏል። ይህ የሚያሳየው ውጤታማ አስተዳደር እና ታሪካዊ ድንበር መኖር ብቻውን በቂ እንዳልሆነ እና እውቅና ማግኘት በስምምነት፣ በቀጠናዊ ፖለቲካ እና በዲፕሎማሲያዊ ድጋፍ ላይ በእጅጉ የተመሰረተ መሆኑን ነው።
የአፍሪካ ህብረት በ2005 ወደ አካባቢው አጣሪ ቡድን ልኮ የሶማሌላንድ ጥያቄ በቅኝ ግዛት ድንበር እና በቀድሞ ነጻነቷ ላይ የተመሰረተ ታሪካዊ መነሻ እንዳለው ቢገነዘብም፣ አሁንም ድረስ ለሶማሊያ ሉዓላዊነት እና የግዛት አንድነት ቅድሚያ መስጠትን መርጧል። በርካታ የአፍሪካ ሀገራት ሶማሌላንድን እውቅና መስጠት በሌሎች አካባቢዎች የመገንጠል ጥያቄዎችን ሊያነሳሳ ይችላል የሚል ስጋት አላቸው። ሶማሌላንድ በበኩሏ የድሮውን ድንበር መመለስ እንጂ አዲስ ድንበር መፍጠር አይደለም ስትል ምላሽ ትሰጣለች።
ሶማሌላንድ በቅኝ ግዛት ድንበር እና በቀድሞ ነጻነት ላይ የተመሰረተ ጠንካራ የህግ መከራከሪያ ብታቀርብም፣ የኤርትራን ተሞክሮ ስንመለከት የህግ ትንታኔ ብቻውን እውቅናን እንደማያመጣ መገንዘብ ይቻላል። ሶማሌላንድ ከሶማሊያ ጋር የደረሰችበት ምንም አይነት ስምምነት ባለመኖሩ፣ የእውቅና ጉዳይ አሁንም ድረስ አለም አቀፍ ተቋማት የድሮዋን ሉዓላዊ ሀገር ዳግም መመለስ አድርገው ይቀበሉታል ወይስ የሶማሊያን የግዛት አንድነት የሚፈታተን ድርጊት አድርገው ይቆጥሩታል የሚለው ጉዳይ የፈተና መድረክ ሆኖ ቀጥሏል።
4 days ago
ከታች ያለው የአርሚ 70 አባል የፃፈው ነው!
ሸረሪና! አርሚ 70!
"አንድ የአርሚ 70 አባል የሆነ የቤተሰቤ አባል ከሱዳን ወሰን ሸረሪና አካባቢ ደውሎልኝ ነበር።
ዛሬ ማታ ሑመራ እንገባለን፤ ተዘጋጁ የሚል ትዕዛዝ ወርዶልናል።
ሙሉ ሌሊት ስንጓዝ አድረናል። ሲነጋ አካባቢ የመጣበት ቦታ የማይታወቅ፣ ከሰማይ ሲወርድ ምንም ድምፅ የሌለውና መሬት ላይ ሲያርፍ ብቻ ድምፅ የሚያሰማ ተኩስ ይፈነዳ ጀመር። ሩቅ ሆነን ስናያቸው የነበሩ የመካናይዝድ ተሽከርካሪዎች በሙሉ ማለት ይቻላል ተቃጥለው እሳት ሲነድ ብቻ ይታያል።
እግረኛ የሆንነው ደግሞ የመካናይዝድ ተሽከርካሪዎች እየጠፋ እንደሆነ ስለተረዳን ሁላችንም ተበታትነናል። ከእኛ ጋር አንድ የሬዲዮ ኦፕሬተር እና የሬዲዮ መገናኛ የያዘ አለ፤ ነገር ግን ከኃላፊዎች የደረሳቸው ምንም ዓይነት መረጃ የለም።
ለኢትዮጵያ መከላከያ ኃይል እጃችንን እንዳንሰጥ በፊታችን የሚታይ ሠራዊት የለም። ጨንቆናል!
እኔም የምናገረው ጠፍቶኛል!!
የህወሓት ቡድን አፈቀላጤዎች ስራችሁን ስለጀመራችሁ እንኳን ደስ አላችሁ።
via wedi shambel
Seledadotio
Seledadotio
ሸረሪና! አርሚ 70!
"አንድ የአርሚ 70 አባል የሆነ የቤተሰቤ አባል ከሱዳን ወሰን ሸረሪና አካባቢ ደውሎልኝ ነበር።
ዛሬ ማታ ሑመራ እንገባለን፤ ተዘጋጁ የሚል ትዕዛዝ ወርዶልናል።
ሙሉ ሌሊት ስንጓዝ አድረናል። ሲነጋ አካባቢ የመጣበት ቦታ የማይታወቅ፣ ከሰማይ ሲወርድ ምንም ድምፅ የሌለውና መሬት ላይ ሲያርፍ ብቻ ድምፅ የሚያሰማ ተኩስ ይፈነዳ ጀመር። ሩቅ ሆነን ስናያቸው የነበሩ የመካናይዝድ ተሽከርካሪዎች በሙሉ ማለት ይቻላል ተቃጥለው እሳት ሲነድ ብቻ ይታያል።
እግረኛ የሆንነው ደግሞ የመካናይዝድ ተሽከርካሪዎች እየጠፋ እንደሆነ ስለተረዳን ሁላችንም ተበታትነናል። ከእኛ ጋር አንድ የሬዲዮ ኦፕሬተር እና የሬዲዮ መገናኛ የያዘ አለ፤ ነገር ግን ከኃላፊዎች የደረሳቸው ምንም ዓይነት መረጃ የለም።
ለኢትዮጵያ መከላከያ ኃይል እጃችንን እንዳንሰጥ በፊታችን የሚታይ ሠራዊት የለም። ጨንቆናል!
እኔም የምናገረው ጠፍቶኛል!!
የህወሓት ቡድን አፈቀላጤዎች ስራችሁን ስለጀመራችሁ እንኳን ደስ አላችሁ።
via wedi shambel
Seledadotio
Seledadotio
5 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) ከኢራን ብሔራዊ የደህንነት ምክር ቤት የወጣው አዲስ ማስጠንቀቂያ በቀጠናው ያለውን ወታደራዊ ፍጥጫ ወደ ላቀ ደረጃ አሸጋግሮታል።
ቴህራን ባወጣችው መግለጫ፣ አሜሪካ በደቡባዊ የኢራን ወደቦች ላይ የጣለችውን የባህር ኃይል እገዳ የምትቀጥል ከሆነ፣ በሆርሙዝ የባህር ሰርጥ ላይ ያለው ቁጥጥር ይበልጥ እንደሚጠበቅና ከዚህ በተጨማሪም ሌሎች የባህር መተላለፊያ ሰርጦች ሊዘጉ ወይም ሊቆለፉ እንደሚችሉ ዝታለች።
ኢራን በመግለጫዋ ላይ የሌሎቹን የባህር ሰርጦች ስም በግልጽ ባትጠቅስም፣ ከቴህራን ጋር የጠበቀ ወዳጅነት ያላቸው ሁቲዎች የሚቆጣጠሩት የባቢል መንደብ የባህር ሰርጥ እና የኤደን ባህረ ሰላጤ መሆናቸውን በቀላሉ መረዳት ይቻላል።
የኢራን መንግስት አሜሪካ እገዳውን የምትገፋበት ከሆነ የዓለም አቀፉ የኃይል (የነዳጅ) ገበያ ክፉኛ እንደሚናወጥ አስታውቋል። መግለጫው የአሜሪካ መራጮችንም ጭምር ያነጣጠረ ሲሆን፣ በዓለም አቀፍ የነዳጅ ገበያ ላይ የሚፈጠር ማንኛውም መስተጓጎል በአሜሪካ የአገር ውስጥ የነዳጅ ዋጋ ላይ ቀጥተኛ ተጽዕኖ እንደሚያሳድር የታወቀ ነው።
በዚህም አኳኋን ቴህራን አዲስ የመደራደሪያ እና የማስፈራሪያ እኩልዮሽ በመዘርጋት፣ ለአሜሪካ ማንኛውም እርምጃ የኃይል ምላሽ ለመስጠት የተዘጋጀች ይመስላል።
ይህ የኢራን ማስፈራሪያ የመጣው፣ አሜሪካ እና እስራኤል የኢራንን የኃይል እና የነዳጅ መሰረተ ልማቶች ላይ ጥቃት ለመሰንዘር አዲስ ወታደራዊ ዘመቻ ሊከፍቱ ይችላሉ የሚሉ ግምቶች በበረቱበት ወቅት መሆኑ ዘገባውን ይበልጥ አሳሳቢ አድርጎታል።
ቴህራን ባወጣችው መግለጫ፣ አሜሪካ በደቡባዊ የኢራን ወደቦች ላይ የጣለችውን የባህር ኃይል እገዳ የምትቀጥል ከሆነ፣ በሆርሙዝ የባህር ሰርጥ ላይ ያለው ቁጥጥር ይበልጥ እንደሚጠበቅና ከዚህ በተጨማሪም ሌሎች የባህር መተላለፊያ ሰርጦች ሊዘጉ ወይም ሊቆለፉ እንደሚችሉ ዝታለች።
ኢራን በመግለጫዋ ላይ የሌሎቹን የባህር ሰርጦች ስም በግልጽ ባትጠቅስም፣ ከቴህራን ጋር የጠበቀ ወዳጅነት ያላቸው ሁቲዎች የሚቆጣጠሩት የባቢል መንደብ የባህር ሰርጥ እና የኤደን ባህረ ሰላጤ መሆናቸውን በቀላሉ መረዳት ይቻላል።
የኢራን መንግስት አሜሪካ እገዳውን የምትገፋበት ከሆነ የዓለም አቀፉ የኃይል (የነዳጅ) ገበያ ክፉኛ እንደሚናወጥ አስታውቋል። መግለጫው የአሜሪካ መራጮችንም ጭምር ያነጣጠረ ሲሆን፣ በዓለም አቀፍ የነዳጅ ገበያ ላይ የሚፈጠር ማንኛውም መስተጓጎል በአሜሪካ የአገር ውስጥ የነዳጅ ዋጋ ላይ ቀጥተኛ ተጽዕኖ እንደሚያሳድር የታወቀ ነው።
በዚህም አኳኋን ቴህራን አዲስ የመደራደሪያ እና የማስፈራሪያ እኩልዮሽ በመዘርጋት፣ ለአሜሪካ ማንኛውም እርምጃ የኃይል ምላሽ ለመስጠት የተዘጋጀች ይመስላል።
ይህ የኢራን ማስፈራሪያ የመጣው፣ አሜሪካ እና እስራኤል የኢራንን የኃይል እና የነዳጅ መሰረተ ልማቶች ላይ ጥቃት ለመሰንዘር አዲስ ወታደራዊ ዘመቻ ሊከፍቱ ይችላሉ የሚሉ ግምቶች በበረቱበት ወቅት መሆኑ ዘገባውን ይበልጥ አሳሳቢ አድርጎታል።
Sponsored by
Surafel
5 days ago
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሀገራዊ ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ጉዳዮች ዙሪያ ባደረጉት ቃለ ምልልስ ያነሷቸው ዋና ዋና ጉዳዮች፡-
👉 ሰኔ 15 ቀን 2011 ዓ.ም በከፍተኛ ወታደራዊና የመንግሥት አመራሮች ላይ የተፈጸመው ግድያ በኢትዮጵያ ፖለቲካ ትምምን ውስጥ ጠባሳ ፈጥሯል፡፡
👉 የፖለቲካ መተማመን በጣም እንዲቀዘቅዝ አድርጓል፣ በሰዎች መካከል አብረህ እየኖርክ፤ እየሰራህ፤ እየተሰበሰብክ የመተማመን ዝንባሌው በእጅጉ እንዲቀንስ አደርጓል፡፡
👉 አብረህ ስለ ሀገር ከምትመክረው ሰው አደጋ ያጋጥመኛል ብለህ እያሰብክ መምከር በእጅጉ ትምምንን የሚቀንስ ጉዳይ ስለሆነ እንደ አንድ ጠባሳ የሚታይ ክስተት ነው፡፡
👉 ክስተቱ የኢትዮጵያን የፖለቲካ ባህል አበላሽቶታል፤ ከንግግር ከውይይት ይልቅ በመሳሪያና በጉልበት ግለሰቦችን በማፈንና በመግደል ስልጣን የመጎናጸፍ ልምምድን የሚያስቀጥል ጠባሳ ሆኗል፡፡
👉 ገዳይንም፣ ሟችንም ሁለቱንም ወገኖች በጀግንነት ያወሳ የፖለቲካ ትርክት የታየበት ክስተት ነው፤ ይህንን አሁንም ቆም ብለን ማየት ይገባናል፡፡
👉 ታሪክን እየመረጥን፣ እያንሻፈፍን እና በፈለግነው መንገድ የማቆየት የትርክት ስብራት ጉዳይ አሁን ላለንበት አጠቃላይ ውጥንቅጥ ዋናው መሰረት ነው፡፡
👉 በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ እስካሁን ከሚስተዋለው ከዚህ ውጥንቅጥ ወጥተን፤ ታሪክን እንዳለ አስቀምጠን ከመልካሙም ከስህተቱም መማር ይገባናል፡፡
👉 አሁን እዚህ እንደ ዋዛ በብሄርተኝነት ስሜት በአውራጃዊነት ስሜት ታሪክን አንሻፍፈን ብንጽፍ፣ ብንናገር ነገ ልጆቻችንን ዋጋ የሚያስከፍል መሆኑን ማሰብ አለመቻል ደግሞ ያሳዝነኛል፡፡
👉 ይሄ ጉዳይ እንዳለ ታሪኩን አስቀምጠህ ከተቀመጠው ታሪክ ተነስተህ በሚኖረው ትንተና የፈለግከውን ነገር ወደ ቀኝ ወደ ግራ ወስደህ መማር ትችላለህ፡፡
👉 ታሪክን ማዛባት ግን እምብዛም ጠቃሚ አይደለም፤ ዛሬ ብቻ ሳይሆን ነገም ዋጋ ያስከፍላል፣ ትውልድ ዋጋ ይከፍልበታል፡፡
👉 እኛ በህይወት እያለን የምናውቀውን ጉዳይ በተንሸዋረረ የታሪክ አረዳድ የምናስቀምጥ ከሆነ እኛ በማንኖርበት ሰዓት የሚኖረው ትወልድ እንዴት እንደሚወስደው አሁን ባለው የኢትዮጵያ ታሪክ መመልከት ይቻላል፡፡
👉 አሁን ያለው የኢትዮጵያ ታሪክ የዚህ የተንሸዋረረ የፖለቲካ ትርክት ውጤት ነው፡፡
👉 ታሪክን እንዳለ ማስቀመጥ ሳይሆን አዛብተን በማስቀመጣችን ምክንያት የሚፈጠር ችግር ነው፤ ከዚያም ሻገር ሲል የፖለቲካ ሴራ ተንታኞች መጠቀሚያም ሆኗል፡፡
👉 ያ ክስተት በተፈጠረበት ወቅት አሚኮን ጠርተን ለሕዝቡ መግለጫ የሰጠነው እዚሁ አዲስ አበባ መሆኑን ታውቃለህ፥ በኋላ ግን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ባህር ዳር ሆነው መግለጫ ሰጡ በሚል የሴራ ተንታኔ ተቀይሯል፡፡
👉 እንደዚህ ያለ ከእውነት የተፋታ፤ ለዛሬም ለነገም የማይበጅ፤ የሚሸነገል የሚዋሽ ነገር ጥፋት ብቻ ነው የሚያመጣው፡፡
👉 ክስተቱ እንደ ጥቁር ጠባሳ የሚወሰድ መጥፎ ክስተት ነው፡፡
በአቤል ነዋይ
👉 ሰኔ 15 ቀን 2011 ዓ.ም በከፍተኛ ወታደራዊና የመንግሥት አመራሮች ላይ የተፈጸመው ግድያ በኢትዮጵያ ፖለቲካ ትምምን ውስጥ ጠባሳ ፈጥሯል፡፡
👉 የፖለቲካ መተማመን በጣም እንዲቀዘቅዝ አድርጓል፣ በሰዎች መካከል አብረህ እየኖርክ፤ እየሰራህ፤ እየተሰበሰብክ የመተማመን ዝንባሌው በእጅጉ እንዲቀንስ አደርጓል፡፡
👉 አብረህ ስለ ሀገር ከምትመክረው ሰው አደጋ ያጋጥመኛል ብለህ እያሰብክ መምከር በእጅጉ ትምምንን የሚቀንስ ጉዳይ ስለሆነ እንደ አንድ ጠባሳ የሚታይ ክስተት ነው፡፡
👉 ክስተቱ የኢትዮጵያን የፖለቲካ ባህል አበላሽቶታል፤ ከንግግር ከውይይት ይልቅ በመሳሪያና በጉልበት ግለሰቦችን በማፈንና በመግደል ስልጣን የመጎናጸፍ ልምምድን የሚያስቀጥል ጠባሳ ሆኗል፡፡
👉 ገዳይንም፣ ሟችንም ሁለቱንም ወገኖች በጀግንነት ያወሳ የፖለቲካ ትርክት የታየበት ክስተት ነው፤ ይህንን አሁንም ቆም ብለን ማየት ይገባናል፡፡
👉 ታሪክን እየመረጥን፣ እያንሻፈፍን እና በፈለግነው መንገድ የማቆየት የትርክት ስብራት ጉዳይ አሁን ላለንበት አጠቃላይ ውጥንቅጥ ዋናው መሰረት ነው፡፡
👉 በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ እስካሁን ከሚስተዋለው ከዚህ ውጥንቅጥ ወጥተን፤ ታሪክን እንዳለ አስቀምጠን ከመልካሙም ከስህተቱም መማር ይገባናል፡፡
👉 አሁን እዚህ እንደ ዋዛ በብሄርተኝነት ስሜት በአውራጃዊነት ስሜት ታሪክን አንሻፍፈን ብንጽፍ፣ ብንናገር ነገ ልጆቻችንን ዋጋ የሚያስከፍል መሆኑን ማሰብ አለመቻል ደግሞ ያሳዝነኛል፡፡
👉 ይሄ ጉዳይ እንዳለ ታሪኩን አስቀምጠህ ከተቀመጠው ታሪክ ተነስተህ በሚኖረው ትንተና የፈለግከውን ነገር ወደ ቀኝ ወደ ግራ ወስደህ መማር ትችላለህ፡፡
👉 ታሪክን ማዛባት ግን እምብዛም ጠቃሚ አይደለም፤ ዛሬ ብቻ ሳይሆን ነገም ዋጋ ያስከፍላል፣ ትውልድ ዋጋ ይከፍልበታል፡፡
👉 እኛ በህይወት እያለን የምናውቀውን ጉዳይ በተንሸዋረረ የታሪክ አረዳድ የምናስቀምጥ ከሆነ እኛ በማንኖርበት ሰዓት የሚኖረው ትወልድ እንዴት እንደሚወስደው አሁን ባለው የኢትዮጵያ ታሪክ መመልከት ይቻላል፡፡
👉 አሁን ያለው የኢትዮጵያ ታሪክ የዚህ የተንሸዋረረ የፖለቲካ ትርክት ውጤት ነው፡፡
👉 ታሪክን እንዳለ ማስቀመጥ ሳይሆን አዛብተን በማስቀመጣችን ምክንያት የሚፈጠር ችግር ነው፤ ከዚያም ሻገር ሲል የፖለቲካ ሴራ ተንታኞች መጠቀሚያም ሆኗል፡፡
👉 ያ ክስተት በተፈጠረበት ወቅት አሚኮን ጠርተን ለሕዝቡ መግለጫ የሰጠነው እዚሁ አዲስ አበባ መሆኑን ታውቃለህ፥ በኋላ ግን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ባህር ዳር ሆነው መግለጫ ሰጡ በሚል የሴራ ተንታኔ ተቀይሯል፡፡
👉 እንደዚህ ያለ ከእውነት የተፋታ፤ ለዛሬም ለነገም የማይበጅ፤ የሚሸነገል የሚዋሽ ነገር ጥፋት ብቻ ነው የሚያመጣው፡፡
👉 ክስተቱ እንደ ጥቁር ጠባሳ የሚወሰድ መጥፎ ክስተት ነው፡፡
በአቤል ነዋይ
5 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) በኢትዮጵያ ላለፉት ሶስት ዓመታት ሲካሄድ የቆየው ሀገራዊ የምክክር ሂደት አሁን ላይ ሀገሪቱን ክፉኛ ወደሚያወዛግቡ ፖለቲካዊ ጥያቄዎች መግባቱን ተከትሎ፣ ታዋቂው የኢኮኖሚ እና የፖለቲካ ተንታኝ አቶ ክቡር ገና የሂደቱን መነሻ ሀሳብ አጥብቀው ተቹ። አቶ ክቡር ዛሬ ባወጡት ጽሁፍ፣ ጉባኤው መጀመር የነበረበት "ኢትዮጵያውያን በጋራ መገንባት የሚፈልጉት የወደፊት ዕጣ ፈንታ ምንድን ነው?" በሚለው ጥያቄ ሆኖ ሳለ፣ ሂደቱ ግን "ኢትዮጵያውያንን የሚከፋፍላቸው ምንድን ነው?" በሚል የተሳሳተ የመነሻ ጥያቄ መጀመሩን አስምረውበታል።
የምክክር ኮሚሽኑ በአሁኑ ወቅት የሀገሪቱን ሰንደቅ ዓላማ፣ ምልክቶች፣ የወደፊቱን የህገ-መንግስት ቅርጽ፣ ፓርላማዊ ወይስ ፕሬዝዳንታዊ ስርዓት፣ የአዲስ አበባ አስተዳደር ባለቤትነት፣ የፌደራሊዝም፣ የማንነት፣ የታሪክ እና የስልጣን ጉዳዮችን ወደ ጠረጴዛ አምጥቷል። እነዚህ ጥያቄዎች እጅግ አስፈላጊ ቢሆኑም፣ ኢትዮጵያውያን በከፍተኛ ደረጃ የማይግባቡባቸው ጉዳዮች መሆናቸውን አቶ ክቡር ያስረዳሉ።
የፖለቲካ ፍልስፍና እንደሚያሳየው፣ ሀገራት በህገ-መንግስት ወይም በሰንደቅ ዓላማ ብቻ በአንድነት ሊቆሙ አይችሉም። ይልቁንም ህዝቦች ልዩነቶቻቸው እንደተጠበቁ ሆነው የጋራ መጻኢ ጊዜን ለመምረጥ ሲወስኑ ብቻ ነው ሀገራት ሊቀጥሉ የሚችሉት። ይህ ምርጫ ደግሞ ከህገ-መንግስት ቀረጻ በፊት ሊመጣ የሚገባው እንጂ በኋላ የሚመጣ አለመሆኑን ተንታኙ ይሞግታሉ። የምክክር ሂደቱ ግን ይህንን ተፈጥሯዊ ቅደም ተከተል የገለበጠው ይመስላል።
የምክክር ሂደቱ ዋነኛ ሀገራዊ ቅራኔዎችን በመለየት እና ተወካዮችን በማሰባሰብ መግባባት ላይ መድረስ ይቻላል የሚል ፍልስፍናን የተከተለ ይመስላል። ነገር ግን ታሪክ እንደሚያሳየው፣ ሰዎች ከጥልቅ ቅራኔዎቻቸው በመነሳት አንድነትን ሲያገኙ አይታይም፤ ይልቁንም የየራሳቸውን አቋም በበለጠ ሁኔታ መከላከልን ነው የሚማሩት። በታሪክ አተረጓጎም ክርክር የሚጀምር ውይይት፣ በተሻለ የተብራራ የታሪክ ልዩነትን በማስገኘት ያበቃል። ተሳታፊዎች ይበልጥ ተማምነው ሳይሆን፣ እርስ በርስ በተሻለ ሁኔታ ተረድተው ብቻ ሊወጡ ይችላሉ። አቶ ክቡር እንደሚሉት፣ መደማመጥ ማለት ሀገር መገንባት ማለት አይደለም።
የምክክር ሂደቱ የመጀመሪያ ምዕራፍ የህዝብን ብሶት ከመሰብሰብ ይልቅ የህዝብን ምኞት ማሰባሰብ ነበረበት። እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ኢትዮጵያ እንደ አንድ ሀገር ለምን መቀጠል እንዳለባት፣ ለየብቻ ሊገነባ የማይችል ነገር ግን በጋራ ሊገነባ የሚችል የወደፊት ጊዜ ምን እንደሆነ፣ እንዲሁም ለዚህ የጋራ ዕጣ ፈንታ ለመጠየቅ ሳይሆን ለመሰዋት ዝግጁ የሆነው ምን እንደሆነ ቢጠየቅ ኖሮ አቅጣጫው በተቀየረ ነበር። እነዚህ ጥያቄዎች ቢነሱ ኖሮ ውይይቱ ከባለቤትነት ይልቅ ወደ ዓላማ፣ ከመብት ይልቅ ወደ ኃላፊነት እንዲሁም ከትናንት ይልቅ ወደ ነገ በተሸጋገረ ነበር።
የሂደቱን ተአማኒነት አደጋ ላይ የሚጥለው ሌላው ትልቅ ፈተና፣ መሳተፍ የነበረባቸው ወሳኝ አካላት በጉባኤው ውስጥ አለመኖራቸው ነው። ታዋቂ የተቃዋሚ ፖለቲካ መሪዎች በእስር ላይ ይገኛሉ፣ አንዳንዶቹ በስደት ላይ ናቸው፣ ሌሎች ደግሞ በትጥቅ ትግል ውስጥ ተሳትፈዋል። ለኢትዮጵያ የተለየ ራዕይ ያላቸው በርካታ ተጽእኖ ፈጣሪ ምሁራን እና የፖለቲካ ተዋናዮች ሂደቱን እንደራሳቸው አድርገው አይመለከቱትም። ሰላም ብዙ ጊዜ የሚደራደረው አስቀድመው በሚግባቡ ሰዎች መካከል ሳይሆን፣ በመካከላቸው ጥልቅ ያለመተማመን ባለባቸው አካላት መካከል በመሆኑ፣ ወሳኝ ድምጽ ያላቸው አካላት ሁሉ በውጪ ከመቅረት ይልቅ በአዳራሹ ውስጥ መገኘታቸው እጅግ አስፈላጊ መሆኑን ጽሁፉ ያትታል።
ታሪክ የሚያስታውሰው ስንት ውይይቶች እንደተካሄዱ፣ ስንት አጀንዳዎች እንደተሰበሰቡ ወይም ስንት ሪፖርቶች እንደወጡ አይደለም። አቶ ክቡር ገና በመደምደሚያቸው እንዳሰፈሩት፣ ታሪክ የሚዘክረው "ምክክሩ የኢትዮጵያን የጋራ ብሔራዊ ማንነት አጠናክሯል ወይስ በቀላሉ የኢትዮጵያን አለመግባባቶች በተሻለ ሁኔታ አደራጅቷል?" የሚለውን ብቻ ነው። ተሳታፊዎች ከጉባኤው ሲወጡ "አሁን በጋራ ምን ዓይነት የወደፊት ጊዜ መገንባት እንችላለን?" ብለው ከጠየቁ፣ ሀገርን የመገን ባት እጅግ ወሳኝ ስራ ተጀምሯል ማለት ነው። ይህ ደግሞ የምክክር ጉባኤው ሊጀምርበት ይገባ የነበረው ትክክለኛው የመጀመሪያ ጥያቄ መሆን ነበረበት።
የምክክር ኮሚሽኑ በአሁኑ ወቅት የሀገሪቱን ሰንደቅ ዓላማ፣ ምልክቶች፣ የወደፊቱን የህገ-መንግስት ቅርጽ፣ ፓርላማዊ ወይስ ፕሬዝዳንታዊ ስርዓት፣ የአዲስ አበባ አስተዳደር ባለቤትነት፣ የፌደራሊዝም፣ የማንነት፣ የታሪክ እና የስልጣን ጉዳዮችን ወደ ጠረጴዛ አምጥቷል። እነዚህ ጥያቄዎች እጅግ አስፈላጊ ቢሆኑም፣ ኢትዮጵያውያን በከፍተኛ ደረጃ የማይግባቡባቸው ጉዳዮች መሆናቸውን አቶ ክቡር ያስረዳሉ።
የፖለቲካ ፍልስፍና እንደሚያሳየው፣ ሀገራት በህገ-መንግስት ወይም በሰንደቅ ዓላማ ብቻ በአንድነት ሊቆሙ አይችሉም። ይልቁንም ህዝቦች ልዩነቶቻቸው እንደተጠበቁ ሆነው የጋራ መጻኢ ጊዜን ለመምረጥ ሲወስኑ ብቻ ነው ሀገራት ሊቀጥሉ የሚችሉት። ይህ ምርጫ ደግሞ ከህገ-መንግስት ቀረጻ በፊት ሊመጣ የሚገባው እንጂ በኋላ የሚመጣ አለመሆኑን ተንታኙ ይሞግታሉ። የምክክር ሂደቱ ግን ይህንን ተፈጥሯዊ ቅደም ተከተል የገለበጠው ይመስላል።
የምክክር ሂደቱ ዋነኛ ሀገራዊ ቅራኔዎችን በመለየት እና ተወካዮችን በማሰባሰብ መግባባት ላይ መድረስ ይቻላል የሚል ፍልስፍናን የተከተለ ይመስላል። ነገር ግን ታሪክ እንደሚያሳየው፣ ሰዎች ከጥልቅ ቅራኔዎቻቸው በመነሳት አንድነትን ሲያገኙ አይታይም፤ ይልቁንም የየራሳቸውን አቋም በበለጠ ሁኔታ መከላከልን ነው የሚማሩት። በታሪክ አተረጓጎም ክርክር የሚጀምር ውይይት፣ በተሻለ የተብራራ የታሪክ ልዩነትን በማስገኘት ያበቃል። ተሳታፊዎች ይበልጥ ተማምነው ሳይሆን፣ እርስ በርስ በተሻለ ሁኔታ ተረድተው ብቻ ሊወጡ ይችላሉ። አቶ ክቡር እንደሚሉት፣ መደማመጥ ማለት ሀገር መገንባት ማለት አይደለም።
የምክክር ሂደቱ የመጀመሪያ ምዕራፍ የህዝብን ብሶት ከመሰብሰብ ይልቅ የህዝብን ምኞት ማሰባሰብ ነበረበት። እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ኢትዮጵያ እንደ አንድ ሀገር ለምን መቀጠል እንዳለባት፣ ለየብቻ ሊገነባ የማይችል ነገር ግን በጋራ ሊገነባ የሚችል የወደፊት ጊዜ ምን እንደሆነ፣ እንዲሁም ለዚህ የጋራ ዕጣ ፈንታ ለመጠየቅ ሳይሆን ለመሰዋት ዝግጁ የሆነው ምን እንደሆነ ቢጠየቅ ኖሮ አቅጣጫው በተቀየረ ነበር። እነዚህ ጥያቄዎች ቢነሱ ኖሮ ውይይቱ ከባለቤትነት ይልቅ ወደ ዓላማ፣ ከመብት ይልቅ ወደ ኃላፊነት እንዲሁም ከትናንት ይልቅ ወደ ነገ በተሸጋገረ ነበር።
የሂደቱን ተአማኒነት አደጋ ላይ የሚጥለው ሌላው ትልቅ ፈተና፣ መሳተፍ የነበረባቸው ወሳኝ አካላት በጉባኤው ውስጥ አለመኖራቸው ነው። ታዋቂ የተቃዋሚ ፖለቲካ መሪዎች በእስር ላይ ይገኛሉ፣ አንዳንዶቹ በስደት ላይ ናቸው፣ ሌሎች ደግሞ በትጥቅ ትግል ውስጥ ተሳትፈዋል። ለኢትዮጵያ የተለየ ራዕይ ያላቸው በርካታ ተጽእኖ ፈጣሪ ምሁራን እና የፖለቲካ ተዋናዮች ሂደቱን እንደራሳቸው አድርገው አይመለከቱትም። ሰላም ብዙ ጊዜ የሚደራደረው አስቀድመው በሚግባቡ ሰዎች መካከል ሳይሆን፣ በመካከላቸው ጥልቅ ያለመተማመን ባለባቸው አካላት መካከል በመሆኑ፣ ወሳኝ ድምጽ ያላቸው አካላት ሁሉ በውጪ ከመቅረት ይልቅ በአዳራሹ ውስጥ መገኘታቸው እጅግ አስፈላጊ መሆኑን ጽሁፉ ያትታል።
ታሪክ የሚያስታውሰው ስንት ውይይቶች እንደተካሄዱ፣ ስንት አጀንዳዎች እንደተሰበሰቡ ወይም ስንት ሪፖርቶች እንደወጡ አይደለም። አቶ ክቡር ገና በመደምደሚያቸው እንዳሰፈሩት፣ ታሪክ የሚዘክረው "ምክክሩ የኢትዮጵያን የጋራ ብሔራዊ ማንነት አጠናክሯል ወይስ በቀላሉ የኢትዮጵያን አለመግባባቶች በተሻለ ሁኔታ አደራጅቷል?" የሚለውን ብቻ ነው። ተሳታፊዎች ከጉባኤው ሲወጡ "አሁን በጋራ ምን ዓይነት የወደፊት ጊዜ መገንባት እንችላለን?" ብለው ከጠየቁ፣ ሀገርን የመገን ባት እጅግ ወሳኝ ስራ ተጀምሯል ማለት ነው። ይህ ደግሞ የምክክር ጉባኤው ሊጀምርበት ይገባ የነበረው ትክክለኛው የመጀመሪያ ጥያቄ መሆን ነበረበት።
6 days ago
ይሄን ምስኪን ምን አድርግ ነው የምትሉት?
#ethiopia | የናቲ ገጠመኝ በግለሰብ ደረጃ የተፈጸመ ቅጥ አልባ ድርጊት ብቻ ሳይሆን በአሁኑ ወቅት በማህበራዊ ሚዲያ ላይ "እይታን" ለመቃረም ሲባል የሚደረግ የዘመኑ ልክፍት ነው።
ይህ ድርጊት ከቀልድነት አልፎ በሰዎች ሰላማዊ ህይወት ላይ የሚፈጸም ጥቃት ነው!
በመሠረቱ ፕራንክ የሚሉት ነገር ለዛ ቢስ ጨዋታ ነው ነገር ግን ፤ ይሁን ይደረግ ከተባለም (አድራጊውንም ሆነ ተደራጊውን) መጨረሻው የማያሳቅቅ እና የሰዎችን ስሜት የማይጎዳ መሆን ይገበዋል፤ አሁን አሁን ግን ሰዎችን ማዋከብ፣ ማስደንገጥ እና ስነ-ልቦናዊ ጫና ማድረስ እንደ መዝናኛ እየተቆጠረ ነው።
የናቲ ድንጋጤ እና ፊቱ ላይ ይነበብ የነበረው ጭንቀት ለነሱ "ጥሩ የቲክቶክ ቪዲዮ" ሲሆን፣ ለሱ ግን ትርጉሙ ሌላ ነው።
ሌላው የደንብ ልብስን አላግባብ መጠቀምስ ይቻላል ወይ?
አንደኛው ግለሰብ የፖሊስ ልብስ(የሚመስል) ለብሶ መምጣቱ ድርጊቱን ከስነ-ምግባር ግድፈት አልፎ ከባድ የህግ ጥሰት ያደርገዋል።
ዜጎች በጸጥታ አስከባሪዎች ላይ ሊኖራቸው የሚገባውን እምነት የሚሸረሽር እና የመንግስትን የደንብ ልብስ ለግል የሶሻል ሚዲያ ትርፍ ማዋረድ ነው።
የሰውን ልጅ ሰላም ነስቶ የሚገኝ ላይክ ዋጋው ስንት ነው?
መፍትሄው እና መማር ያለብን እሴት
፣ ከዚህ ሁሉ ጫጫታ እና የሰዎችን ክብር ከሚረግጥ አዝማሚያ ወጥተን ሰውን በማክበር ረገድ እንድናስብ ያስፈልጋል።
ጥበብ ሰውን በማክበር እንጂ ሰውን በማዋረድ ውስጥ የለችም።
የሚዲያ ተጠቃሚውም ቢሆን እንዲህ አይነት ሰብዓዊ ክብርን የሚጋፉ ይዘቶችን ከማበረታታት፣ ከማየት እና ከማጋራት በመቆጠብ ይህንን እኩይ ተግባር ሊያወግዘው ይገባል። ሰውን ማክበር ኋላቀርነት ሳይሆን የስልጣኔ ሁሉ ቁንጮ ነው።
በያፌት ገ/ህይወት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#ethiopia | የናቲ ገጠመኝ በግለሰብ ደረጃ የተፈጸመ ቅጥ አልባ ድርጊት ብቻ ሳይሆን በአሁኑ ወቅት በማህበራዊ ሚዲያ ላይ "እይታን" ለመቃረም ሲባል የሚደረግ የዘመኑ ልክፍት ነው።
ይህ ድርጊት ከቀልድነት አልፎ በሰዎች ሰላማዊ ህይወት ላይ የሚፈጸም ጥቃት ነው!
በመሠረቱ ፕራንክ የሚሉት ነገር ለዛ ቢስ ጨዋታ ነው ነገር ግን ፤ ይሁን ይደረግ ከተባለም (አድራጊውንም ሆነ ተደራጊውን) መጨረሻው የማያሳቅቅ እና የሰዎችን ስሜት የማይጎዳ መሆን ይገበዋል፤ አሁን አሁን ግን ሰዎችን ማዋከብ፣ ማስደንገጥ እና ስነ-ልቦናዊ ጫና ማድረስ እንደ መዝናኛ እየተቆጠረ ነው።
የናቲ ድንጋጤ እና ፊቱ ላይ ይነበብ የነበረው ጭንቀት ለነሱ "ጥሩ የቲክቶክ ቪዲዮ" ሲሆን፣ ለሱ ግን ትርጉሙ ሌላ ነው።
ሌላው የደንብ ልብስን አላግባብ መጠቀምስ ይቻላል ወይ?
አንደኛው ግለሰብ የፖሊስ ልብስ(የሚመስል) ለብሶ መምጣቱ ድርጊቱን ከስነ-ምግባር ግድፈት አልፎ ከባድ የህግ ጥሰት ያደርገዋል።
ዜጎች በጸጥታ አስከባሪዎች ላይ ሊኖራቸው የሚገባውን እምነት የሚሸረሽር እና የመንግስትን የደንብ ልብስ ለግል የሶሻል ሚዲያ ትርፍ ማዋረድ ነው።
የሰውን ልጅ ሰላም ነስቶ የሚገኝ ላይክ ዋጋው ስንት ነው?
መፍትሄው እና መማር ያለብን እሴት
፣ ከዚህ ሁሉ ጫጫታ እና የሰዎችን ክብር ከሚረግጥ አዝማሚያ ወጥተን ሰውን በማክበር ረገድ እንድናስብ ያስፈልጋል።
ጥበብ ሰውን በማክበር እንጂ ሰውን በማዋረድ ውስጥ የለችም።
የሚዲያ ተጠቃሚውም ቢሆን እንዲህ አይነት ሰብዓዊ ክብርን የሚጋፉ ይዘቶችን ከማበረታታት፣ ከማየት እና ከማጋራት በመቆጠብ ይህንን እኩይ ተግባር ሊያወግዘው ይገባል። ሰውን ማክበር ኋላቀርነት ሳይሆን የስልጣኔ ሁሉ ቁንጮ ነው።
በያፌት ገ/ህይወት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
7 days ago
ከፍተኛ ግብር የሰበሰቡ ተሸለሙ
"...ምን ማለት ነው?"
(ሙሼ ሰሙ)
#ethiopia | "ከፍተኛ ግብር የሰበሰቡ ተሸለሙ" የሚል ዜና በስፋት እየተዘገበ ነው። ከፍተኛ ግብር ሰበሰቡ ማለት ምን ማለት ነው ?! አንጻሩስ ምንድን ነው ? በጀት ነው ? ኮታ ነው? ወይስ የትም ፍጪው ዲቄቱን አምጭው ነው ? ከበጀት በላይ ማትረፍ እንጂ ከበጀት በላይ ግብር መሰብሰብስ እንዴት ይቻላል? ይህ አዲስ ግኝት ነው?
በደሞዝ ተቀጥሮ የሚሰራ ሰራተኛ "ውጤታማ ሲሆን" ጉርሻ ( Bonus) ከመስጠትና ደሞዙን ከማሳደግ አልፎ ለተቋሙ አገልግሎት የሚውል ቢሆንም በየዓመቱ ተሽከርካሪ መለወጥ የትኛው መንግስታዊ አሰራርና ደንብ እንደሚፈቅድ የውጭ ኦዲተር መጠየቅ የሚገባው ጉዳይ ይመስለኛል ?
ወደ ዋነኛ ጉዳዬ ልመለስ ።
እርግጥ ነው። ነጋዴ ንብረቱን ላለማጣትና ድርጅቱን ላለመዝጋት ሲል ጥሪቱንና አቅሙን አሟጦ እስኪጨርስና ቤቱ እስኪከረቸም ድረስ ከበጀትም ከኮታም በላይ እጥፍ ድርብ ግብር በማስከፈል ከበጀት በላይ ገንዘብ መሰብሰብ ይቻላል። ተችሏልም። ጥያቄው ግን እስከመቼ የሚለው ነው ?!
በዚህ መንገድ የመንግስት ገቢ አንድ ሺ ፐርሰንት ሊያድግና ሊመነደግ ይችላል። በኮታና በነሲብ ግብር የመሰብሰብ ዘመቻ በሂደት የነጋዴውን ገቢ እያዳከመና ትርፉን እያቀጨጨ ከመሄድ ውጭ ጤናማ የንግድ፣ የግብይይትና የግብር ስርዓት ሊፈጥር አይችልም። ንግድ ፈቃዱን በሰልፍ የሚመልሰውና ድብብቆሽ የሚጫወተው ነጋዴም ለዚህ ክስተት ሕያው ምስክር ነው። ለምን ቢባል ንግድ ለጽድቅ የሚሰራ ስራ አይደለም።
ለማንም ግልጽ እንደሚሆነው በጤናማ መንገድና በሕግ አግባብ የሚነግድ፣ የሚሰራና የሚያመርት ሰው (ካልከሰረ በስተቀር) ማትረፍ ብቻ ሳይሆን ከትርፉ ጥሪት በመቋጠርና አቅሙን በማጎልበት ንግዱን በማስፋፋት፣ የስራ እድል መፍጠርና ወደ ሚቀጥለው ከፍተኛ የኢኮኖሚ መደብ ( Economic Class) መሸጋገር መቻል አለበት።
ጤናማ የኢኮኖሚ እድገትና ሽግግር፣ የንግድና የግብር ስርዓት መስተጋብር ማለት ይህው ብቻ ነው። ነጋዴውን አሟጦ በማስገበር ማቀጨጭና በሂደት ከገበያ እንዲወጣ ማድረግ የልማት፣ የእድገትና የምርታማነት እንቅፋት ከመሆን ባሻገር ሕገ ወጥነትና የጓሮ በር ድርድር እንዲስፋፋ በር መክፈት ብቻ ነው። በገሃዱ ዓለምም እየሆነ ያለውም ይህው ነው።
ጤናማ የግብር ስርዓት ንግድና ነጋዴው እንዲያብቡ አመቺ ሁኔታን በመፍጠር አምራቹን፣ ባለኢንዱስትሪውን፣ ቸርቻሪውን አከፋፋዩንና አስመጭውን በቁጥርም በአቅምም እንዲጎለብቱ በማገዝ ከሚፈጠረው ሰፊ የንግድ አቅምና ከሚሳለጠው የምርትና የግብይይት ስርዓት ከእያንዳንዱ ነጋዴ ላይ ተመጣጣኝ ግብር በመሰብሰብ በቅንጅት እንደ ሀገር ማደግ ይቻላል።
ይህ እውን መሆን የሚቻለው ነጋዴው በቂ ትርፍ አትርፎና ጥሪት ቋጥሮ የማምረት አቅሙን በማጎለብት ፣ ፋብሪካውንና ኢንዱስትሪውን በማሳድግ፣ የስራ እድልና አቅርቦትን በማስፋፋት እምቅ ሃይሉንና አቅሙን መጠቀም የማይገድበው፣ በተለይ ከገቢው ጋር የሚመጣጠን ግብር መገበር ሲችል ብቻ ነው።
በጥቅሉ በነሲብ፣ በጅምላና በኮታ የሚጣል ግብር የነጋዴውን ማህበረሰብ አቅም በማሟጠጥና ኪሱን በማራቆት በሂደት ተያይዞ መውደቅን እንጂ ተያይዞ ማደግን አያመጣም። "በነጻ ውድድር ገበያ የሚመራ" ነገር ግን ነጋዴ የሌለበት ወይም ሕገ ወጥነትና ጥገኛ ነጋዴ የተንሰራፋበት ሀገር መፍጠር ነው።
በተደጋጋሚ የሚነሳው የመንግስት ገቢና የሀገሪቱ አጠቃላይ ምርት አለመጣጣም መንስኤ ነጋዴው በቂ ግብር ባለመክፈሉ ብቻ ሳይሆን ሳይቀረጥ ወደ ሀገር ውስጥ የሚገባ ሕገ ወጥ የገቢ ሸቀጥ መበራከት፣ ቫት የማይጎበኘው አቅርቦት መስፋፋት፣ መንግስት ማግኘት የሚገባው ነገር ግን በአስፈጻሚ አካላት ሙሰኝነት ባክኖ የሚቀር ገቢና በሕገ ወጥ ነጋዴዎችና በሙሰኞች መመሳጠር አየር ላይ ተበልቶ የሚቀረው ገቢ ከሚከፈለው ግብር እጅግ የላቀ መሆን ነው ። ( ማብቂያ የሌለው የገቢ የሚያቀጣጥሉ በገቢ አቅም በላይ ወጭ መልመድ፣ ብክነት፣ ዝርክርከነትና በአቅም አለመኖር ብቻውን ሊነሳ የሚገባው ጉዳይ ነው)
የመንግስት አስፈጻሚዎች ላይ የነሲብ አስገዳጅ ኮታ በመጣል ኮታቸውን ለመሟላት በየሱቁ፣ በየድርጅቱና በየፋብሪካው እየዞሩ ነጋዴውን ያልሸጠከውን ሸጠሃል። ያላመረትከውን አምርተሃል። ያላገኘውን ትርፍት አግኝተሃል በማለት አቅሉን በመሳት ወደ ሕገ ወጥነት እንዲያመራ ከመግፋት ይልቅ መንግስት የራሱን ጓዳ (የገቢዎችንና የጉምሩክን) አሰራር በመመርመርና በሙስና ተድበስብሶ አየር ላይ የሚቀረውን ግብር በመታደግ ገቢውን ማሳደግ፣ ወጭውን በመቆጣጠርና ቁጠባ በመለማመድ ገቢውን በእጥፍ ድርብ ማሳደግ ይችላል።
ነጋዴውንም ከመዋከብ፣ ከመሳደድ በመታደግ ተስፋ ከመቁረጥና የሙሰኞች መጫወቻ ከመሆን ተገላግሎ እፎይታ አግኝቶና ተረጋግቶ አዕምሮውን ለስራ፣ ጊዜውንና ጉልበቱን ለፈጠራና ለምርታማነት፣ ገንዘቡን ለእድገት እንዲጠቀም በማገዝ እየተፈራሩና እየተጠራጠሩ በጨለማ ከመዳከር ይልቅ የስራ ጊዜን ውጤታማ፣ የነጋዴውም ሆነ የሸማቹን ህይወት በተስፋ የተሞላና ብሩህ ማድረግ ይቻላል።
"...ምን ማለት ነው?"
(ሙሼ ሰሙ)
#ethiopia | "ከፍተኛ ግብር የሰበሰቡ ተሸለሙ" የሚል ዜና በስፋት እየተዘገበ ነው። ከፍተኛ ግብር ሰበሰቡ ማለት ምን ማለት ነው ?! አንጻሩስ ምንድን ነው ? በጀት ነው ? ኮታ ነው? ወይስ የትም ፍጪው ዲቄቱን አምጭው ነው ? ከበጀት በላይ ማትረፍ እንጂ ከበጀት በላይ ግብር መሰብሰብስ እንዴት ይቻላል? ይህ አዲስ ግኝት ነው?
በደሞዝ ተቀጥሮ የሚሰራ ሰራተኛ "ውጤታማ ሲሆን" ጉርሻ ( Bonus) ከመስጠትና ደሞዙን ከማሳደግ አልፎ ለተቋሙ አገልግሎት የሚውል ቢሆንም በየዓመቱ ተሽከርካሪ መለወጥ የትኛው መንግስታዊ አሰራርና ደንብ እንደሚፈቅድ የውጭ ኦዲተር መጠየቅ የሚገባው ጉዳይ ይመስለኛል ?
ወደ ዋነኛ ጉዳዬ ልመለስ ።
እርግጥ ነው። ነጋዴ ንብረቱን ላለማጣትና ድርጅቱን ላለመዝጋት ሲል ጥሪቱንና አቅሙን አሟጦ እስኪጨርስና ቤቱ እስኪከረቸም ድረስ ከበጀትም ከኮታም በላይ እጥፍ ድርብ ግብር በማስከፈል ከበጀት በላይ ገንዘብ መሰብሰብ ይቻላል። ተችሏልም። ጥያቄው ግን እስከመቼ የሚለው ነው ?!
በዚህ መንገድ የመንግስት ገቢ አንድ ሺ ፐርሰንት ሊያድግና ሊመነደግ ይችላል። በኮታና በነሲብ ግብር የመሰብሰብ ዘመቻ በሂደት የነጋዴውን ገቢ እያዳከመና ትርፉን እያቀጨጨ ከመሄድ ውጭ ጤናማ የንግድ፣ የግብይይትና የግብር ስርዓት ሊፈጥር አይችልም። ንግድ ፈቃዱን በሰልፍ የሚመልሰውና ድብብቆሽ የሚጫወተው ነጋዴም ለዚህ ክስተት ሕያው ምስክር ነው። ለምን ቢባል ንግድ ለጽድቅ የሚሰራ ስራ አይደለም።
ለማንም ግልጽ እንደሚሆነው በጤናማ መንገድና በሕግ አግባብ የሚነግድ፣ የሚሰራና የሚያመርት ሰው (ካልከሰረ በስተቀር) ማትረፍ ብቻ ሳይሆን ከትርፉ ጥሪት በመቋጠርና አቅሙን በማጎልበት ንግዱን በማስፋፋት፣ የስራ እድል መፍጠርና ወደ ሚቀጥለው ከፍተኛ የኢኮኖሚ መደብ ( Economic Class) መሸጋገር መቻል አለበት።
ጤናማ የኢኮኖሚ እድገትና ሽግግር፣ የንግድና የግብር ስርዓት መስተጋብር ማለት ይህው ብቻ ነው። ነጋዴውን አሟጦ በማስገበር ማቀጨጭና በሂደት ከገበያ እንዲወጣ ማድረግ የልማት፣ የእድገትና የምርታማነት እንቅፋት ከመሆን ባሻገር ሕገ ወጥነትና የጓሮ በር ድርድር እንዲስፋፋ በር መክፈት ብቻ ነው። በገሃዱ ዓለምም እየሆነ ያለውም ይህው ነው።
ጤናማ የግብር ስርዓት ንግድና ነጋዴው እንዲያብቡ አመቺ ሁኔታን በመፍጠር አምራቹን፣ ባለኢንዱስትሪውን፣ ቸርቻሪውን አከፋፋዩንና አስመጭውን በቁጥርም በአቅምም እንዲጎለብቱ በማገዝ ከሚፈጠረው ሰፊ የንግድ አቅምና ከሚሳለጠው የምርትና የግብይይት ስርዓት ከእያንዳንዱ ነጋዴ ላይ ተመጣጣኝ ግብር በመሰብሰብ በቅንጅት እንደ ሀገር ማደግ ይቻላል።
ይህ እውን መሆን የሚቻለው ነጋዴው በቂ ትርፍ አትርፎና ጥሪት ቋጥሮ የማምረት አቅሙን በማጎለብት ፣ ፋብሪካውንና ኢንዱስትሪውን በማሳድግ፣ የስራ እድልና አቅርቦትን በማስፋፋት እምቅ ሃይሉንና አቅሙን መጠቀም የማይገድበው፣ በተለይ ከገቢው ጋር የሚመጣጠን ግብር መገበር ሲችል ብቻ ነው።
በጥቅሉ በነሲብ፣ በጅምላና በኮታ የሚጣል ግብር የነጋዴውን ማህበረሰብ አቅም በማሟጠጥና ኪሱን በማራቆት በሂደት ተያይዞ መውደቅን እንጂ ተያይዞ ማደግን አያመጣም። "በነጻ ውድድር ገበያ የሚመራ" ነገር ግን ነጋዴ የሌለበት ወይም ሕገ ወጥነትና ጥገኛ ነጋዴ የተንሰራፋበት ሀገር መፍጠር ነው።
በተደጋጋሚ የሚነሳው የመንግስት ገቢና የሀገሪቱ አጠቃላይ ምርት አለመጣጣም መንስኤ ነጋዴው በቂ ግብር ባለመክፈሉ ብቻ ሳይሆን ሳይቀረጥ ወደ ሀገር ውስጥ የሚገባ ሕገ ወጥ የገቢ ሸቀጥ መበራከት፣ ቫት የማይጎበኘው አቅርቦት መስፋፋት፣ መንግስት ማግኘት የሚገባው ነገር ግን በአስፈጻሚ አካላት ሙሰኝነት ባክኖ የሚቀር ገቢና በሕገ ወጥ ነጋዴዎችና በሙሰኞች መመሳጠር አየር ላይ ተበልቶ የሚቀረው ገቢ ከሚከፈለው ግብር እጅግ የላቀ መሆን ነው ። ( ማብቂያ የሌለው የገቢ የሚያቀጣጥሉ በገቢ አቅም በላይ ወጭ መልመድ፣ ብክነት፣ ዝርክርከነትና በአቅም አለመኖር ብቻውን ሊነሳ የሚገባው ጉዳይ ነው)
የመንግስት አስፈጻሚዎች ላይ የነሲብ አስገዳጅ ኮታ በመጣል ኮታቸውን ለመሟላት በየሱቁ፣ በየድርጅቱና በየፋብሪካው እየዞሩ ነጋዴውን ያልሸጠከውን ሸጠሃል። ያላመረትከውን አምርተሃል። ያላገኘውን ትርፍት አግኝተሃል በማለት አቅሉን በመሳት ወደ ሕገ ወጥነት እንዲያመራ ከመግፋት ይልቅ መንግስት የራሱን ጓዳ (የገቢዎችንና የጉምሩክን) አሰራር በመመርመርና በሙስና ተድበስብሶ አየር ላይ የሚቀረውን ግብር በመታደግ ገቢውን ማሳደግ፣ ወጭውን በመቆጣጠርና ቁጠባ በመለማመድ ገቢውን በእጥፍ ድርብ ማሳደግ ይችላል።
ነጋዴውንም ከመዋከብ፣ ከመሳደድ በመታደግ ተስፋ ከመቁረጥና የሙሰኞች መጫወቻ ከመሆን ተገላግሎ እፎይታ አግኝቶና ተረጋግቶ አዕምሮውን ለስራ፣ ጊዜውንና ጉልበቱን ለፈጠራና ለምርታማነት፣ ገንዘቡን ለእድገት እንዲጠቀም በማገዝ እየተፈራሩና እየተጠራጠሩ በጨለማ ከመዳከር ይልቅ የስራ ጊዜን ውጤታማ፣ የነጋዴውም ሆነ የሸማቹን ህይወት በተስፋ የተሞላና ብሩህ ማድረግ ይቻላል።
8 days ago
በሆነ በዘመን የቀረውን እኔን የመለሰ አልበም!
የአህመድ ተሸመ (ዲንቢ) “ጊዜ አይሄድም”!
ተስፋዬ እሸቱ (ረ/ፕሮፌሰር)
#ethiopia | መቸም የአህመድ ተሾመ (ዲንቢ) ድንቅ የዜማ ደራሲነት ሰብዕና ለድርድር የሚቀርብ አይደለም፡፡ ለራሱ የሠራቸውን ዘግየት እናድርግና ለሌሎች የሙያ አጋሮቹ ሠርቶላቸው በብዙኋን አድማጮች ዘንድ ሰፊ ተቀባይነትን ያገኙትን የዜማ ድርሰቶቹን እንዘርዝር ብንል ጊዜም ሥፍራም አይበቃንም፡፡
እንደው ከግምታችን በላይ ስለሆነው ስለዲንቢ የላቀ የዜማ ደራሲነት ሰብዕና መሠረታዊ ግንዛቤ ሊያስጨብጠን ቢችል ግን ጥቂቱን ብቻ ከዚህ እንደሚከተለው እዘረዝርላችኋለሁ፡—
ለአሊ ቢራና ሄለን በርሄ - “ሲያዴ”፤ ለፀሀዬ ዮሐንስ - “ማን ልበልሽ”፤ ለማዲንጎ አፈወርቅ - “ላላተርፍ”፤ ለብዙአየሁ ደምሴ - “የህልሜ ንግስት”፤ ለዘቢባ ግርማ - “ገራገር”፤ ለኢሳያስ ታምራት - “እያዳነ ያማል”፤ ለታረቀኝ ሙሉ - “ስሚያቸው”፤ ለሚኪያስ ቸርነት - “ግርማ ሞገሴ”፤ ለሃይማኖት ግርማ - “ከዚራ ቁ-2”፤ ለግርማ ተፈራ - “ልዩ”፤ ለሀመልማል አባተ - “ሀሴት”፤ እና የመሳሰሉቱን የአህመድ ዲንቢን የዜማ ፈጠራዎች ከብዙ በጥቂቱ ማስታወስ ይቻላል፡፡
አንዳንድ ሙዚቃዎች ለጆሮ ብቻ አይሰሩም፤ ለስሜት ይደርሳሉ፤ ዛሬ ተሰርተው ግን ትዝታችንን ይመልሱልናል፡፡
አንዳንድ ዜማዎች፣ በውስጣችን የተከረቸሙ የጊዜ በሮችን ያንኳኳሉ፤ ይከፍታሉምም፡፡ በሮቹ ሲከፈቱ ደግሞ የተዘነጉ ፊቶች፣ የተለየናቸው ጓደኞች፣ የተራመድንባቸውን ጎዳናዎች… ብቻ ምኑ ቅጡ ትላንታችንን እንደ መጽሀፍ ይገልጡልናል፡፡ በሆነ ዘመን የቀረውን ማንነታችንን እንደገና ይመልሱልናል።
አህመድ ተሾመ (ዲንቢ) ከ14 ዓመታት በኋላ በአዲስ አልበሙ ሲመለስ፣ እኔ የሰማሁት የአዳዲስ ዜማዎች ስብስብን አይደለም። አንድ በሆነ ዘመን የነበረ የዜማ ሰዋሰውና በዚሁ ዜማ ምክንያት የተሰፋ፣ የምናፍቀውን ዘመን የመለሰልኝ ያህል ነው የተሰማኝ፡፡
ያ የኔ ዘመን የምለው “ዘጠናዎቹ”ን ነው፡፡
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተማሪ ሆኜ የገባሁት በ1997 ዓ.ም. ነው። አይ፣ ተማሪነት! እንዴት ያለ ጣፋጭ፣ እንዴት ያለ የማይደገም ዘመን ነበር! ያ ዘመን ለእኔ የወጣትነት ወርቃማ ጠዋት ነበር። ዓለምን እንደ አዲስ ማየት የጀመርኩበት፤ ከተማዋን፣ ሕይወትን፣ ፍቅርን፣ ሐሳብንና ነፃነትን ለመጀመሪያ ጊዜ በሙሉ ልብ ያጣጣምኩበት ዘመን ነበር።
ያ ዘመን ከጓደኞቸ ጋር እንደፈለግን የኖርንበት ዘመን ነበር። በአደባባይ የተከራከርንበት፣ አለምን የጠየቅንበት፣ መንግሥትን ለመጀመሪያ ጊዜ የተቃወምንበት፣ ነፃነትን ያየንበት፣ ዜማን ያጣጣምንበት ወቅት ነበር። ያ ዘመን “ዘጠናዎቹ” ነበር፡፡
ያንን ዘመን ሁሌም እናፍቀዋለሁ፤ ምናልባትም የምናፍቀው ዘመኑን ራሱን አይደለም፤ በዚያ ዘመን ውስጥ የነበርነውን እሱን፣ እሷን፣እኔን፣እኛን ነው። እንደገና እንዲመጣም እመኛለሁ።
ማርሴል ፕሩስት የተባለ ፈረንሳያዊ የልብ ወለድ ጸሀፊና ሀያሲ ጥልቅ የሆነን ትዝታ አስበን ለማስታወስ በምናደርገው ጥረት አይመለስም፤ ነገር ግን የስሜት ሕዋሳችን በሚነካ አንድ ድንገተኛ ልምድ ሊቀሰቀስ ይችላል ይላል፡፡ ሙዚቃም ከእነዚህ የትዝታ ቀስቃሾች መካከል እጅግ ኃይለኛው ሳይሆን አይቀርም።
በዚህ ረገድ እንደ አህመድ ተሾመ ጥንቅቅ ተደርጎ የተሰራ ዜማ የተረሳ ግን ተደበቀ ስሜትን ይቀሰቅሳል፤ የጠፋ የሚመስለውን የዜማ ስልተ ምት ይመልሳል፤ በዘመን ጥላ ሥር ተደብቆ የኖረ ማንነት እንደገና ያነቃቃል።
በ1990ዎቹ የኢትዮጵያ ሙዚቃ የራሱ የሆነ የዜማ ሰዋሰው፣ ቀለምና የአወራረድ ለዛ ነበረው። ያ ዘመን ለእኔ ሙዚቃን ከመስማት ወደ ማዳመጥ የተሸጋገርኩበት ጊዜ ነው። ስለዚህ የዚያ ዘመን ዜማዎች በጆሮዬ ብቻ ተደምጠው አልቀሩም፤ በማንነቴ ውስጥ ህያው ናቸው።
እኔ የሙዚቃ ባለሙያ አይደለሁም፤ ሙዚቃን ግን በልቤ አዳምጠዋለሁ። በእኔ የዜማ አረዳድ፣ የዚያ ዘመን የዜማ አሠራሮች በቀላሉ የሚደገሙ አይደሉም። ምክንያቱም ዜማው የተፈጠረው በድምፅ ብቻ ሳይሆን፣ በዘመኑ መንፈስም ጭምር ነው። ከዚያ በኋላ የመጡት ዘመናት የራሳቸውን የሙዚቃ ቋንቋ ፈጥረዋል።
ያው ዘመን ሲለወጥ የዜማ ሰዋሰውም የሚለወጥ ይመስለኛል፡፡ ይህም የሥነ ጥበብ ተፈጥሯዊ ሂደት ነው፤ ዋናው ጉዳይ ግን በ1990ዎቹና ከዚያ በኋላ በመጡት ዜማዎች መካከል የተቋረጠ ነገር ያለ ይመስለኛል፡፡ መቆራረጡ ለሙዚቃ ባለሙያዎች ትልቅ የጥናት ርዕስ የሚሆንም ነው፡፡
ታዲያ የአህመድ ተሾመ አዲስ አልበም፣ የ1990ዎቹን የዜማ መንፈስ አገኘሁበት፤ የቀድሞውን በቀጥታ ሳይደግም፣ ያንን ለዛ በአዲስ ስልተ ምት የቀነበበ ዜማ ሆኖ አዳመጥኩት። ጉዳዩን ሳይንቲፊካሊ መግለጽ ባልችልም ልቤ ግን አልበሙ በዚያን ጊዜና በዛሬው የሙዚቃ ዘመን መካከል የተዘረጋ የዜማ ድልድይ እንደሆነ ይነግረኛል።
በአጠቃላይ ለእኔ፣ የአህመድ ተሾመ (ዲንቢ) ጊዜ አይሄድም አዲስ አልበም የአዳዲስ ዜማዎች ስብስብ ብቻ አይደለም። ካለፈ ጊዜና ትዝታ ጋር የተደረገ ውይይት ነው፤ ትናንትን ከዛሬ ጋር ያስታረቀ የዜማ ድልድይ ነው፤ በዘጠናዎቹ የቀረውን እኔን የመለሰ አልበም ነው። ይመችሽ ዲንቢ!!
ካላመናችሁኝ ደግሞ ከአዲስ አልበሙ መካከል "ጊዜ አይሄድም"፣"አይሽና"፣ "ይረፍዳል" እና "ህልም ነው" አድመጣችሁ ፍረዱኝ፤ ካጠፋሁ እኔ ሳልሆን ዲንቢ ይቀጣል፡፡
የአህመድ ተሸመ (ዲንቢ) “ጊዜ አይሄድም”!
ተስፋዬ እሸቱ (ረ/ፕሮፌሰር)
#ethiopia | መቸም የአህመድ ተሾመ (ዲንቢ) ድንቅ የዜማ ደራሲነት ሰብዕና ለድርድር የሚቀርብ አይደለም፡፡ ለራሱ የሠራቸውን ዘግየት እናድርግና ለሌሎች የሙያ አጋሮቹ ሠርቶላቸው በብዙኋን አድማጮች ዘንድ ሰፊ ተቀባይነትን ያገኙትን የዜማ ድርሰቶቹን እንዘርዝር ብንል ጊዜም ሥፍራም አይበቃንም፡፡
እንደው ከግምታችን በላይ ስለሆነው ስለዲንቢ የላቀ የዜማ ደራሲነት ሰብዕና መሠረታዊ ግንዛቤ ሊያስጨብጠን ቢችል ግን ጥቂቱን ብቻ ከዚህ እንደሚከተለው እዘረዝርላችኋለሁ፡—
ለአሊ ቢራና ሄለን በርሄ - “ሲያዴ”፤ ለፀሀዬ ዮሐንስ - “ማን ልበልሽ”፤ ለማዲንጎ አፈወርቅ - “ላላተርፍ”፤ ለብዙአየሁ ደምሴ - “የህልሜ ንግስት”፤ ለዘቢባ ግርማ - “ገራገር”፤ ለኢሳያስ ታምራት - “እያዳነ ያማል”፤ ለታረቀኝ ሙሉ - “ስሚያቸው”፤ ለሚኪያስ ቸርነት - “ግርማ ሞገሴ”፤ ለሃይማኖት ግርማ - “ከዚራ ቁ-2”፤ ለግርማ ተፈራ - “ልዩ”፤ ለሀመልማል አባተ - “ሀሴት”፤ እና የመሳሰሉቱን የአህመድ ዲንቢን የዜማ ፈጠራዎች ከብዙ በጥቂቱ ማስታወስ ይቻላል፡፡
አንዳንድ ሙዚቃዎች ለጆሮ ብቻ አይሰሩም፤ ለስሜት ይደርሳሉ፤ ዛሬ ተሰርተው ግን ትዝታችንን ይመልሱልናል፡፡
አንዳንድ ዜማዎች፣ በውስጣችን የተከረቸሙ የጊዜ በሮችን ያንኳኳሉ፤ ይከፍታሉምም፡፡ በሮቹ ሲከፈቱ ደግሞ የተዘነጉ ፊቶች፣ የተለየናቸው ጓደኞች፣ የተራመድንባቸውን ጎዳናዎች… ብቻ ምኑ ቅጡ ትላንታችንን እንደ መጽሀፍ ይገልጡልናል፡፡ በሆነ ዘመን የቀረውን ማንነታችንን እንደገና ይመልሱልናል።
አህመድ ተሾመ (ዲንቢ) ከ14 ዓመታት በኋላ በአዲስ አልበሙ ሲመለስ፣ እኔ የሰማሁት የአዳዲስ ዜማዎች ስብስብን አይደለም። አንድ በሆነ ዘመን የነበረ የዜማ ሰዋሰውና በዚሁ ዜማ ምክንያት የተሰፋ፣ የምናፍቀውን ዘመን የመለሰልኝ ያህል ነው የተሰማኝ፡፡
ያ የኔ ዘመን የምለው “ዘጠናዎቹ”ን ነው፡፡
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተማሪ ሆኜ የገባሁት በ1997 ዓ.ም. ነው። አይ፣ ተማሪነት! እንዴት ያለ ጣፋጭ፣ እንዴት ያለ የማይደገም ዘመን ነበር! ያ ዘመን ለእኔ የወጣትነት ወርቃማ ጠዋት ነበር። ዓለምን እንደ አዲስ ማየት የጀመርኩበት፤ ከተማዋን፣ ሕይወትን፣ ፍቅርን፣ ሐሳብንና ነፃነትን ለመጀመሪያ ጊዜ በሙሉ ልብ ያጣጣምኩበት ዘመን ነበር።
ያ ዘመን ከጓደኞቸ ጋር እንደፈለግን የኖርንበት ዘመን ነበር። በአደባባይ የተከራከርንበት፣ አለምን የጠየቅንበት፣ መንግሥትን ለመጀመሪያ ጊዜ የተቃወምንበት፣ ነፃነትን ያየንበት፣ ዜማን ያጣጣምንበት ወቅት ነበር። ያ ዘመን “ዘጠናዎቹ” ነበር፡፡
ያንን ዘመን ሁሌም እናፍቀዋለሁ፤ ምናልባትም የምናፍቀው ዘመኑን ራሱን አይደለም፤ በዚያ ዘመን ውስጥ የነበርነውን እሱን፣ እሷን፣እኔን፣እኛን ነው። እንደገና እንዲመጣም እመኛለሁ።
ማርሴል ፕሩስት የተባለ ፈረንሳያዊ የልብ ወለድ ጸሀፊና ሀያሲ ጥልቅ የሆነን ትዝታ አስበን ለማስታወስ በምናደርገው ጥረት አይመለስም፤ ነገር ግን የስሜት ሕዋሳችን በሚነካ አንድ ድንገተኛ ልምድ ሊቀሰቀስ ይችላል ይላል፡፡ ሙዚቃም ከእነዚህ የትዝታ ቀስቃሾች መካከል እጅግ ኃይለኛው ሳይሆን አይቀርም።
በዚህ ረገድ እንደ አህመድ ተሾመ ጥንቅቅ ተደርጎ የተሰራ ዜማ የተረሳ ግን ተደበቀ ስሜትን ይቀሰቅሳል፤ የጠፋ የሚመስለውን የዜማ ስልተ ምት ይመልሳል፤ በዘመን ጥላ ሥር ተደብቆ የኖረ ማንነት እንደገና ያነቃቃል።
በ1990ዎቹ የኢትዮጵያ ሙዚቃ የራሱ የሆነ የዜማ ሰዋሰው፣ ቀለምና የአወራረድ ለዛ ነበረው። ያ ዘመን ለእኔ ሙዚቃን ከመስማት ወደ ማዳመጥ የተሸጋገርኩበት ጊዜ ነው። ስለዚህ የዚያ ዘመን ዜማዎች በጆሮዬ ብቻ ተደምጠው አልቀሩም፤ በማንነቴ ውስጥ ህያው ናቸው።
እኔ የሙዚቃ ባለሙያ አይደለሁም፤ ሙዚቃን ግን በልቤ አዳምጠዋለሁ። በእኔ የዜማ አረዳድ፣ የዚያ ዘመን የዜማ አሠራሮች በቀላሉ የሚደገሙ አይደሉም። ምክንያቱም ዜማው የተፈጠረው በድምፅ ብቻ ሳይሆን፣ በዘመኑ መንፈስም ጭምር ነው። ከዚያ በኋላ የመጡት ዘመናት የራሳቸውን የሙዚቃ ቋንቋ ፈጥረዋል።
ያው ዘመን ሲለወጥ የዜማ ሰዋሰውም የሚለወጥ ይመስለኛል፡፡ ይህም የሥነ ጥበብ ተፈጥሯዊ ሂደት ነው፤ ዋናው ጉዳይ ግን በ1990ዎቹና ከዚያ በኋላ በመጡት ዜማዎች መካከል የተቋረጠ ነገር ያለ ይመስለኛል፡፡ መቆራረጡ ለሙዚቃ ባለሙያዎች ትልቅ የጥናት ርዕስ የሚሆንም ነው፡፡
ታዲያ የአህመድ ተሾመ አዲስ አልበም፣ የ1990ዎቹን የዜማ መንፈስ አገኘሁበት፤ የቀድሞውን በቀጥታ ሳይደግም፣ ያንን ለዛ በአዲስ ስልተ ምት የቀነበበ ዜማ ሆኖ አዳመጥኩት። ጉዳዩን ሳይንቲፊካሊ መግለጽ ባልችልም ልቤ ግን አልበሙ በዚያን ጊዜና በዛሬው የሙዚቃ ዘመን መካከል የተዘረጋ የዜማ ድልድይ እንደሆነ ይነግረኛል።
በአጠቃላይ ለእኔ፣ የአህመድ ተሾመ (ዲንቢ) ጊዜ አይሄድም አዲስ አልበም የአዳዲስ ዜማዎች ስብስብ ብቻ አይደለም። ካለፈ ጊዜና ትዝታ ጋር የተደረገ ውይይት ነው፤ ትናንትን ከዛሬ ጋር ያስታረቀ የዜማ ድልድይ ነው፤ በዘጠናዎቹ የቀረውን እኔን የመለሰ አልበም ነው። ይመችሽ ዲንቢ!!
ካላመናችሁኝ ደግሞ ከአዲስ አልበሙ መካከል "ጊዜ አይሄድም"፣"አይሽና"፣ "ይረፍዳል" እና "ህልም ነው" አድመጣችሁ ፍረዱኝ፤ ካጠፋሁ እኔ ሳልሆን ዲንቢ ይቀጣል፡፡
8 days ago
(ዘ-ሐበሻ ሕይወት) ፈገግታው፣ ቅርበቱ፣ የጓደኝነት ድባቡ... ዛሬ ላይ ቆሞ ለሚያየው በእጅጉ ልብ ይሰብራል። በዚህ ምስል ላይ የምትመለከቷት የ2026ቷ "ሚስ ወርልድ ኢትዮጵያ" ሩት ይርጋለም ስትሆን፣ አጠገቧ የቆመችው ደግሞ የሩትን ታላቅ እህት (ዲዛይነር ቅድሳን ይርጋለምን) ከፍቅረኛዋ እና ከተባባሪዎቿ ጋር አሳግታ በአሰቃቂ ሁኔታ ገድላለች ተብላ በፖሊስ የተያዘችው ዋና ተጠርጣሪ ቅድስት ሙሉቀን ናት።
ከ5 ዓመታት በፊት የገናን በዓል በፍቅር እና በጓደኝነት መንፈስ አብረው ሲያከብሩ፣ ከዓመታት በኋላ ይህችው "ጓደኛ" በምቀኝነት ታውራ የእህቷን ሕይወት በጭካኔ ትቀጥፋለች ብሎ ማን ያስብ ነበር? የሰው ልጅ ልብ እንዴት አይታወቅም! ያኔ አብራ እየሳቀች፣ በውስጧ ግን ጥቁር ጥላቻን እና አደገኛ ሴራን ትፈትል ነበር።
ሩት በልብ ስብራት "ከጠላቴ እኔ እጠነቀቃለሁ፤ ከወዳጄ አንተ ጠብቀኝ" ስትል ያስተላለፈችው መልእክት ምንኛ እውነት መሆኑን ይህ ፎቶ ቁልጭ አድርጎ ያሳየናል። ጠላት ፊቱን አውቆ ሲመጣ መጠንቀቅ ይቻላል፤ ክህደት ግን በወዳጅ ፈገግታ እና በናፍቆት ስም ተጀቡኖ ሲመጣ ማምለጫ የለውም።
እባካችሁ ጓደኛ ስትመርጡ ወደ ውስጣችሁ የምታስገቡትን ሰው ማንነት በሚገባ መርምሩ። ፈገግ ላለላችሁ ሁሉ ልባችሁን አትስጡ!
ፍትህ ለቅድሳን ይርጋለም! 🕊️
ከ5 ዓመታት በፊት የገናን በዓል በፍቅር እና በጓደኝነት መንፈስ አብረው ሲያከብሩ፣ ከዓመታት በኋላ ይህችው "ጓደኛ" በምቀኝነት ታውራ የእህቷን ሕይወት በጭካኔ ትቀጥፋለች ብሎ ማን ያስብ ነበር? የሰው ልጅ ልብ እንዴት አይታወቅም! ያኔ አብራ እየሳቀች፣ በውስጧ ግን ጥቁር ጥላቻን እና አደገኛ ሴራን ትፈትል ነበር።
ሩት በልብ ስብራት "ከጠላቴ እኔ እጠነቀቃለሁ፤ ከወዳጄ አንተ ጠብቀኝ" ስትል ያስተላለፈችው መልእክት ምንኛ እውነት መሆኑን ይህ ፎቶ ቁልጭ አድርጎ ያሳየናል። ጠላት ፊቱን አውቆ ሲመጣ መጠንቀቅ ይቻላል፤ ክህደት ግን በወዳጅ ፈገግታ እና በናፍቆት ስም ተጀቡኖ ሲመጣ ማምለጫ የለውም።
እባካችሁ ጓደኛ ስትመርጡ ወደ ውስጣችሁ የምታስገቡትን ሰው ማንነት በሚገባ መርምሩ። ፈገግ ላለላችሁ ሁሉ ልባችሁን አትስጡ!
ፍትህ ለቅድሳን ይርጋለም! 🕊️
8 days ago
በ108 ዓመታቸው የመኪና መሪ አልለቅም ያሉት የእድሜ ባለፀጋዋ ሜሪ
መሪ በቀላሉ የምንደሰት ከሆነ የማይቻል ነገር የለም ይላሉ
#ethiopia | በአሜሪካ አሪዞና ግዛት ነዋሪ የሆኑት የ108 አመት ባለፀጋዋ መሪ በሰሞኑ የመንጃ ፍቃዳቸውን እስከ ፈረንጆቹ 2033 ድረስ አሳድሰዋል።
108 ዓመታቸው ላይ የሚገኙት መሪ በራሳቸው መኖሪያ ቤት ብቻቸው ከመኖራቸውም በላይ መኪናቸውንም እያሽከረከሩ ይገኛሉ።
ሜሪ ፍሊፕ የተባሉት እኚህ ባለታሪክ ለረጅም እድሜ የበቁበትና ጤናማ የሆኑበትን ምስጢር አካፍለዋል።
በቅርብ ጊዜ የመንጃ ፈቃዳቸውን እስከ ፈረንጆቹ 2033 ድረስ ያደሱት ሜሪ ሙሉ በሙሉ ነፃነታቸውን ጠብቀው በራሳቸው መኖር እንደሚወዱ ይናገራሉ።
ራሴን ሙሉ በሙሉ በራሴ ነው የምንከባከበው የሚሉት ሜሪ በየቀኑ ቀለል ያሉ እንቅስቃሴዎችን መስራት እንደሚያዘወትሩ ይናገራሉ።
ሜሪ እረጅም ዕድሜ የመኖራቸው ምክንያት ሲናገሩ በሕይወታችን ውስጥ ከባድ ችግሮች ሲገጥሙን አዎንታዊ ጎኑን ማየትና ሁልጊዜም ፈገግታን ማብዛት ጤናማ ህይወት መኖር ይቻላል ብለዋል።
በሰው ላይ አለመደገፍ እና የራስን የቤት ውስጥ ስራዎች በተቻለ መጠን በራስ መወጣት ያስፈልጋልም ሲሉ ተናግረዋል።
በቀላሉ ልንደሰትባቸው በሚያስችሉን አነስተኛ ነገሮች ላይ ትኩረት ማድረግ እና ጭንቀትን ማስወገድ እንደሚገባም ተናግረዋል።
ሔኖክ ወ/ገብርኤል
#ethiopia #getutemesgen #getunews #centenarian #drives #longlife #merryfelipe
መሪ በቀላሉ የምንደሰት ከሆነ የማይቻል ነገር የለም ይላሉ
#ethiopia | በአሜሪካ አሪዞና ግዛት ነዋሪ የሆኑት የ108 አመት ባለፀጋዋ መሪ በሰሞኑ የመንጃ ፍቃዳቸውን እስከ ፈረንጆቹ 2033 ድረስ አሳድሰዋል።
108 ዓመታቸው ላይ የሚገኙት መሪ በራሳቸው መኖሪያ ቤት ብቻቸው ከመኖራቸውም በላይ መኪናቸውንም እያሽከረከሩ ይገኛሉ።
ሜሪ ፍሊፕ የተባሉት እኚህ ባለታሪክ ለረጅም እድሜ የበቁበትና ጤናማ የሆኑበትን ምስጢር አካፍለዋል።
በቅርብ ጊዜ የመንጃ ፈቃዳቸውን እስከ ፈረንጆቹ 2033 ድረስ ያደሱት ሜሪ ሙሉ በሙሉ ነፃነታቸውን ጠብቀው በራሳቸው መኖር እንደሚወዱ ይናገራሉ።
ራሴን ሙሉ በሙሉ በራሴ ነው የምንከባከበው የሚሉት ሜሪ በየቀኑ ቀለል ያሉ እንቅስቃሴዎችን መስራት እንደሚያዘወትሩ ይናገራሉ።
ሜሪ እረጅም ዕድሜ የመኖራቸው ምክንያት ሲናገሩ በሕይወታችን ውስጥ ከባድ ችግሮች ሲገጥሙን አዎንታዊ ጎኑን ማየትና ሁልጊዜም ፈገግታን ማብዛት ጤናማ ህይወት መኖር ይቻላል ብለዋል።
በሰው ላይ አለመደገፍ እና የራስን የቤት ውስጥ ስራዎች በተቻለ መጠን በራስ መወጣት ያስፈልጋልም ሲሉ ተናግረዋል።
በቀላሉ ልንደሰትባቸው በሚያስችሉን አነስተኛ ነገሮች ላይ ትኩረት ማድረግ እና ጭንቀትን ማስወገድ እንደሚገባም ተናግረዋል።
ሔኖክ ወ/ገብርኤል
#ethiopia #getutemesgen #getunews #centenarian #drives #longlife #merryfelipe
11 days ago
ፓን-አፍሪካዊ ኃይል የሆነው የመደመር ትውልድ
*******************
ኢትዮጵያ ከጥንት ጀምሮ ለመላው ጥቁር ሕዝቦች የነጻነት ተምሳሌት በመሆን የፓን-አፍሪካኒዝም እሳቤ ተፈጥሯዊ ጉልበት ሆና ቆይታለች።
አውሮፓውያን አህጉሪቱን ለመቀራመት ሲነሡ፣ ኢትዮጵያ በከፍታ ላይ የቆመች እና ሥልጣኔን ያጣጣመች ዕድሜ ጠገብ ሀገር ናት።
ታሪካዊው የዓድዋ ድል እስከ አፍንጫው ታጥቆ የመጣውን የቀኝ ገዢ ኃይል በማንበርከክ የነጭ የበላይነትን እሳቤ ገልብጧል፤ የዓድዋ ድል ለፓን-አፍሪካኒዝም ንቅናቄ አዲስ ጉልበትና የይቻላል መንፈስን አጎናጽፏል።
የትናንቱ የፓን-አፍሪካኒዝም ትግል ማዕከል የፖለቲካ ነጻነት ሲሆን፣ የ21ኛው ክፍለ ዘመን ዋነኛ ትግል የኢኮኖሚ ነጻነትን ማረጋገጥ ነው።
ታላቁ ፓን-አፍሪካኒስት ጁሊየስ ኔሬሬ እንዳስገነዘቡት፣ በመጀመሪያው የአፍሪካ ቅርምት ጎሳን ከጎሳ ያጋጨው የውጭ ኃይል፣ አሁን ደግሞ ሀገርን ከሀገር በማጋጨት አህጉሪቱን ደካማና የተከፋፈለች ለማድረግ ይጥራል። በእርግጥም በመከፋፈል ውስጥ የሚገኝ ክብርም ሆነ ታላቅነት የለም። ከተከፋፈልን ደካሞች እንሆናለን፤ ከተባበርን ግን በእኛ ላይ የሚመጡትን የጣልቃ ገብነት ኃይሎች አሳፍረን መመለስ እንችላለን።
በዚህ ታሪካዊ መጋጠሚያ ላይ፣ የኢትዮጵያ የመደመር ትውልድ ከራሱ አልፎ ቀጣናውን በፓን-አፍሪካዊ መንፈስ ለማስተሳሰር በጽናት ቆሟል። አፍሪካውያን የማይነጣጠሉ እና ዕጣ ፈንታቸው የተሣሠረ፣ የቀኝ ግዛት ድንበርን የሚሻገር የጠበቀ ወንድማማችነት ያላቸው ሕዝቦች ናቸው።
ለአብነት ያህል፣ ፉላኒ ጎሳ ከ19 በላይ የአፍሪካ ሀገራት ውስጥ ሲገኝ፣ አካን በጋና እና አይቮሪኮስት፣ ኦሮሞ በኢትዮጵያ እና ኬንያ፣ አፋር በኢትዮጵያ፣ ኤርትራ እና ጅቡቲ፣ እንዲሁም ሶማሌ በቀጣናው የተለያዩ ሀገራት ተሰራጭቶ ይገኛል።
እ.አ.አ በ1902 በቅኝ ገዢዎች በተደረገ የድንበር ከለላ የበርታ ብሔረሰብ በሁለት ተከፍሎ በሱዳን እና በኢትዮጵያ እንዲኖር ተገዷል። ይህን ሐቅ ጠንቅቆ የተረዳው የመደመር ትውልድ፣ እነዚህን ሕዝቦች በፖለቲካ አጥር ማጠር እንደማይቻል በማመን፣ አፍሪካን እንደ አንድ ሕዝብ በማስተሣሠር የማበልጸግ ኃላፊነትን ወስዷል።
ኢትዮጵያ ይህንን የአብሮነት እና የመደመር እሳቤ በተግባር ለማሳየት የሰፋፊ መሠረተ ልማቶችን ትሥሥር እያከናወነች ትገኛለች። የአፍሪካ ኅብረትን አጀንዳ 2063 ለማሳካት እና ፖለቲካዊ እና ኢኮኖሚያዊ ውህደትን እውን ለማድረግ፣ ለጎረቤት ሀገራት ለምሳሌ ለጅቡቲ፣ ለሱዳን እና ለኬንያ የኤሌክትሪክ ኃይል በማቅረብ የምጣኔ ሀብት ትሥሥር እያፋጠነች ነው።
ከኬንያ ጋር የተዘረጋው የመንገድ መሠረተ ልማት፣ እንዲሁም በውኃ ተፋሰሶች ላይ የሚሠሩ ታላላቅ ግድቦች የዚሁ ታላቅ ፓን-አፍሪካዊ አሰባሳቢ ትሥሥር አካላት ናቸው።
በተጨማሪም የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ባለፉት ሦስት ዐሥርት ዓመታት በሩዋንዳ፣ ላይቤሪያ፣ ሱዳን፣ ብሩንዲ እና ሶማሊያ የሰላም ማስከበር ተልዕኮውን በብቃት በመወጣት አህጉራዊ እና ቀጣናዊ መረጋጋትን አረጋግጧል። ይህም ኢትዮጵያ ለፓን-አፍሪካኒዝም ያላትን የተግባር ቁርጠኝነት ያረጋግጣል።
የ21ኛው ክፍለ ዘመን ፓን-አፍሪካኒዝም አፍሪካውያን በቅኝ ገዢዎች የተሰመሩላቸውን የፖለቲካ ድንበሮች በማንሣት፣ አህጉሪቱን ወደ አንድ የጋራ ነጻ ንግድ ቀጣና በማምራት የኢኮኖሚ ነጻነታቸውን የሚያረጋግጡበት ወሳኝ ምዕራፍ ነው።
የአፍሪካ ሕዝብ ብዛት ከ1.4 ቢሊዮን አልፎ ወደፊት በእጥፍ እንደሚያድግ ሲገመት፣ ይህ ታላቅ አምራች ኃይል እና ሰፊ ገበያ ትልቅ የመልማት አቅም ነው። በተጨማሪም አህጉሪቱ የተፈጥሮ ማዕድን፣ ነዳጅ፣ የውኃ ሀብት እና ሊታረስ የሚችል ሰፊ ለም መሬት፣ እንዲሁም የተለያዩ ማዕድናትን ጨምሮ የተትረፈረፈ ጸጋ ባለቤት ናት።
ከምዕራባውያን ገበያ ጥገኝነት ተላቅቀን ይህንን እምቅ ሀብት በማቀናጀት እና የምናመርተውን ምርት እርስ በርስ ብንለዋወጥ ታላቅ ስኬትን እንጎናጸፋለን።
ኢትዮጵያ ትናንት የፖለቲካ ነፃነት ዓርማ እንደነበረች ሁሉ፣ ዛሬ ደግሞ የመደመር ትውልድን በማስተባበር በቀጣናዊ ሰላም፣ በመሠረተ ልማት ዝርጋታ እና በአህጉራዊ ውህደት የላቀ ሚና በመጫወት ላይ ያለች ጽኑ ፓን-አፍሪካዊ ኃይል ናት።
አዲሱ ትውልድ አፍሪካውያን በመተባበር እና በወንድማማችነት ላይ የተመሠረተ ጠንካራ ኅብረት እንዲፈጥሩ በጽናት የቆመ ኃይል ሆኖ ይቀጥላል፤ ምክንያቱም ለአፍሪካውያን ችግር ብቸኛው መፍትሔ ያለው በራሳቸው በአፍሪካውያን እጅ በመሆኑ ነው።
በአዶኒያስ ወልደአረጋይ
#ethiopia #ebc #hornofafrica #medemer #medemergeneration #diplomacy
*******************
ኢትዮጵያ ከጥንት ጀምሮ ለመላው ጥቁር ሕዝቦች የነጻነት ተምሳሌት በመሆን የፓን-አፍሪካኒዝም እሳቤ ተፈጥሯዊ ጉልበት ሆና ቆይታለች።
አውሮፓውያን አህጉሪቱን ለመቀራመት ሲነሡ፣ ኢትዮጵያ በከፍታ ላይ የቆመች እና ሥልጣኔን ያጣጣመች ዕድሜ ጠገብ ሀገር ናት።
ታሪካዊው የዓድዋ ድል እስከ አፍንጫው ታጥቆ የመጣውን የቀኝ ገዢ ኃይል በማንበርከክ የነጭ የበላይነትን እሳቤ ገልብጧል፤ የዓድዋ ድል ለፓን-አፍሪካኒዝም ንቅናቄ አዲስ ጉልበትና የይቻላል መንፈስን አጎናጽፏል።
የትናንቱ የፓን-አፍሪካኒዝም ትግል ማዕከል የፖለቲካ ነጻነት ሲሆን፣ የ21ኛው ክፍለ ዘመን ዋነኛ ትግል የኢኮኖሚ ነጻነትን ማረጋገጥ ነው።
ታላቁ ፓን-አፍሪካኒስት ጁሊየስ ኔሬሬ እንዳስገነዘቡት፣ በመጀመሪያው የአፍሪካ ቅርምት ጎሳን ከጎሳ ያጋጨው የውጭ ኃይል፣ አሁን ደግሞ ሀገርን ከሀገር በማጋጨት አህጉሪቱን ደካማና የተከፋፈለች ለማድረግ ይጥራል። በእርግጥም በመከፋፈል ውስጥ የሚገኝ ክብርም ሆነ ታላቅነት የለም። ከተከፋፈልን ደካሞች እንሆናለን፤ ከተባበርን ግን በእኛ ላይ የሚመጡትን የጣልቃ ገብነት ኃይሎች አሳፍረን መመለስ እንችላለን።
በዚህ ታሪካዊ መጋጠሚያ ላይ፣ የኢትዮጵያ የመደመር ትውልድ ከራሱ አልፎ ቀጣናውን በፓን-አፍሪካዊ መንፈስ ለማስተሳሰር በጽናት ቆሟል። አፍሪካውያን የማይነጣጠሉ እና ዕጣ ፈንታቸው የተሣሠረ፣ የቀኝ ግዛት ድንበርን የሚሻገር የጠበቀ ወንድማማችነት ያላቸው ሕዝቦች ናቸው።
ለአብነት ያህል፣ ፉላኒ ጎሳ ከ19 በላይ የአፍሪካ ሀገራት ውስጥ ሲገኝ፣ አካን በጋና እና አይቮሪኮስት፣ ኦሮሞ በኢትዮጵያ እና ኬንያ፣ አፋር በኢትዮጵያ፣ ኤርትራ እና ጅቡቲ፣ እንዲሁም ሶማሌ በቀጣናው የተለያዩ ሀገራት ተሰራጭቶ ይገኛል።
እ.አ.አ በ1902 በቅኝ ገዢዎች በተደረገ የድንበር ከለላ የበርታ ብሔረሰብ በሁለት ተከፍሎ በሱዳን እና በኢትዮጵያ እንዲኖር ተገዷል። ይህን ሐቅ ጠንቅቆ የተረዳው የመደመር ትውልድ፣ እነዚህን ሕዝቦች በፖለቲካ አጥር ማጠር እንደማይቻል በማመን፣ አፍሪካን እንደ አንድ ሕዝብ በማስተሣሠር የማበልጸግ ኃላፊነትን ወስዷል።
ኢትዮጵያ ይህንን የአብሮነት እና የመደመር እሳቤ በተግባር ለማሳየት የሰፋፊ መሠረተ ልማቶችን ትሥሥር እያከናወነች ትገኛለች። የአፍሪካ ኅብረትን አጀንዳ 2063 ለማሳካት እና ፖለቲካዊ እና ኢኮኖሚያዊ ውህደትን እውን ለማድረግ፣ ለጎረቤት ሀገራት ለምሳሌ ለጅቡቲ፣ ለሱዳን እና ለኬንያ የኤሌክትሪክ ኃይል በማቅረብ የምጣኔ ሀብት ትሥሥር እያፋጠነች ነው።
ከኬንያ ጋር የተዘረጋው የመንገድ መሠረተ ልማት፣ እንዲሁም በውኃ ተፋሰሶች ላይ የሚሠሩ ታላላቅ ግድቦች የዚሁ ታላቅ ፓን-አፍሪካዊ አሰባሳቢ ትሥሥር አካላት ናቸው።
በተጨማሪም የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ባለፉት ሦስት ዐሥርት ዓመታት በሩዋንዳ፣ ላይቤሪያ፣ ሱዳን፣ ብሩንዲ እና ሶማሊያ የሰላም ማስከበር ተልዕኮውን በብቃት በመወጣት አህጉራዊ እና ቀጣናዊ መረጋጋትን አረጋግጧል። ይህም ኢትዮጵያ ለፓን-አፍሪካኒዝም ያላትን የተግባር ቁርጠኝነት ያረጋግጣል።
የ21ኛው ክፍለ ዘመን ፓን-አፍሪካኒዝም አፍሪካውያን በቅኝ ገዢዎች የተሰመሩላቸውን የፖለቲካ ድንበሮች በማንሣት፣ አህጉሪቱን ወደ አንድ የጋራ ነጻ ንግድ ቀጣና በማምራት የኢኮኖሚ ነጻነታቸውን የሚያረጋግጡበት ወሳኝ ምዕራፍ ነው።
የአፍሪካ ሕዝብ ብዛት ከ1.4 ቢሊዮን አልፎ ወደፊት በእጥፍ እንደሚያድግ ሲገመት፣ ይህ ታላቅ አምራች ኃይል እና ሰፊ ገበያ ትልቅ የመልማት አቅም ነው። በተጨማሪም አህጉሪቱ የተፈጥሮ ማዕድን፣ ነዳጅ፣ የውኃ ሀብት እና ሊታረስ የሚችል ሰፊ ለም መሬት፣ እንዲሁም የተለያዩ ማዕድናትን ጨምሮ የተትረፈረፈ ጸጋ ባለቤት ናት።
ከምዕራባውያን ገበያ ጥገኝነት ተላቅቀን ይህንን እምቅ ሀብት በማቀናጀት እና የምናመርተውን ምርት እርስ በርስ ብንለዋወጥ ታላቅ ስኬትን እንጎናጸፋለን።
ኢትዮጵያ ትናንት የፖለቲካ ነፃነት ዓርማ እንደነበረች ሁሉ፣ ዛሬ ደግሞ የመደመር ትውልድን በማስተባበር በቀጣናዊ ሰላም፣ በመሠረተ ልማት ዝርጋታ እና በአህጉራዊ ውህደት የላቀ ሚና በመጫወት ላይ ያለች ጽኑ ፓን-አፍሪካዊ ኃይል ናት።
አዲሱ ትውልድ አፍሪካውያን በመተባበር እና በወንድማማችነት ላይ የተመሠረተ ጠንካራ ኅብረት እንዲፈጥሩ በጽናት የቆመ ኃይል ሆኖ ይቀጥላል፤ ምክንያቱም ለአፍሪካውያን ችግር ብቸኛው መፍትሔ ያለው በራሳቸው በአፍሪካውያን እጅ በመሆኑ ነው።
በአዶኒያስ ወልደአረጋይ
#ethiopia #ebc #hornofafrica #medemer #medemergeneration #diplomacy
Sponsored by
Surafel
12 days ago
ጽናት
የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ታሪካዊ የለውጥ ጉዞ
1947-2017
#ethiopia | የዶ/ር አሥራት ዓፀደወይን Asrat Atsedeweyn መጽሐፍ በጎንደር ከተማ እየተመረቀ ነው።
ይህ መጽሐፍ መታሰቢያነቱ ስጎንደር ዩኒቨርሲቲ ርስታቸወነ ስሰጡ 59 የጎንደር አርሶ አደሮች፧ እንዲሁም በተለያዩ ዘመናት በአመራርነት፤ በባለሙያነት፤ በሠራተኛነትና በአጋርነት አገልግለው ተቋሙን አሁን ላስበት ታላቅ ደረጃ ኣደረሱ ሞስንነ ባለውለታዎች በሙሉ ይሁን፡፡
***
ከመጽሐፉ ጀርባ (blurb)
ጎንደር የኒቨርሲቲ ኢትዮጵያ ካፈራቻቸው ዩኒቨርሲቲዎች በአንጋፋነት ተርታ የሚመደብ ነው:: በቅርቡም ሰባኛ ዓመቱንና የዩኒቨርሲቲው አስኳል የሆነውን ሆስፒታሉን መቶኛ ዓመት በደማቅ ሁኔታ መዘከሩ ይታወሳል። በዚህ የታሪክ አጋጣሚ የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት የሆነው ዶ/ር አሥራት ዓፀደወይን እነሆ የዩኒቨርሲቲውን ታሪካዊ ጉዞ እርሱ ራሱ በተለያዩ የኃላፊነት እርከኖች ካከናወናቸው ተግባራት ጋር አዛምዶ የሚዘግብ፣ በጠንካራ መረጃ ላይ የተዋቀረ መጽሐፍ አቅርቦልናል።
በዚህም የዩኒቨርሲቲ ቆይታቸውን ከግለ ታሪካቸው ጋር አሰናስለው ለንባብ ያበቁትን የቀደምት የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንቶችን ፈለግ ተከትሏል ማለት ይቻላል። የተቋሙ ታሪካዊ ጉዞ በስኬት የታጀበውን ያህል አያሌ ፈተዎችና ተግዳሮቶችም የተጋረጡበት ነበር። የመጽሐፉ ትልቁ ፋይዳም እነዚህን ስኬቶችና ተግዳሮቶች ነቅሶ በማውጣት ሰፊ ግንዛቤ መስጠቱ ላይ ነው:: በተለይም በደራሲው አመራር የተከናወኑትን P70/100 ዝክረ በዓል ዘርፈ ብዙ ዝግጅቶችና ክንዋኔዎች በዝርዝር ያትታል፤ ዘላቂ እርባናቸውንም ይጠቁማል። በመጨረሻም ከዩኒቨርሲቲ አመራር ተሞክሮው የቀሰማቸውን ትምህርቶች በተመሳሳይ ተቋም ግንባታ ላይ ላሉ ያካፍላል።
ባሕሩ ዘውዴ፣ የታሪክ ኤሜሪተስ ፕሮፌሰር አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ
***
የስኬታማ ተቋማትና የአገር ግንባታ በትውልዶች ቅብብሎሽ፣ በቁርጠኝነትና በመሪዎች እቅድ ላይይመረኮዛል። ዶ/ር አሥራት ዓፀደወይን በዚህ መጽሐፋቸው የጎንደር ዩኒቨርሲቲን የ7ዐ ዓመታት ጉዞ፣ በየዘመናቱ የነበሩ መሪዎችንና ባለድርሻ አካላትን አበርክቶ፣ እንዲሁም የራሳቸውን የኃላፊነት ዘመን ፈተናና ስኬት በጥልቀት አቅርበዋል። በከፍተኛ ትምህርት አመራርነት በነበረኝ የረጅም ጊዜ ኃላፊነት ተቋሙንም ሆነ ደራሲውን በቅርብ እንደማወቄ መጠን፤ ይህ መጽሐፍ ከተጨባጩ ዓለም የተገኘ ጥልቅ እውቀት የሚሰጥ፣ ለመሰል ተቋማት መሪዎችና ተመራማሪዎች ታላቅ ማስተማሪያና ማጣቀሻ እንደሚሆን ሙሉ እምነት አለኝ።
ሳሙኤል ክፍሌ (ዶ/ር)፣ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ኘሬዚደንት
***
ጎንደር ዩኒቨርሲቲ በፈተናዎች ውስጥ ያለፈ ታላቅ ዓለም አቀፍ ተቋም ቢሆንም፣ የነበረው የታሪክ ምዝገባ ግን በቂ አልነበረም:: የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ዶ/ር አሥራት ዓፀደወይን “ጽናት” በተሰኘው መጽሐፋቸው ይህንን የታሪክ ክፍተት ለመሙላት ሞክረዋል። መጽሐፉ፣ ተቋሙ በፈተናዎች ውስጥ አልፎ ለዛሬው ስኬት እንዲበቃ አሻራቸውን ያሳረፉ የቀድሞ ከፍተኛ አመራሮችን እውቅና ይሰጣል። በተጨማሪም፣ ዶ/ር አሥራት ላለፉት ስምንት ዓመታት በኘሬዚዳንትነት ሲያገለግሉ ያጋጠሟቸውን ከባድ ፈተናዎች እንዴት በብቃት እንደተወጧቸውና የዩኒቨርሲቲውን ስኬት እንዴት ማስቀጠል እንደቻሉ ያሳያል። ይህም ለተቋሙ ቀጣይ ጤናማ የአመራር ሽግግርና ለተተኪ አመራሮች ትልቅ ስንቅ የሚሆን ነው።
ዶ/ር ደሳለኝ መንገሻ፣ በኦሃዮ ስቴት ግሎባል ዋን ሄልዝ የኢትዮጵያ ዳይሬክተር እና የቀድሞ የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት
እንኳን ደስ አለህ!
የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ታሪካዊ የለውጥ ጉዞ
1947-2017
#ethiopia | የዶ/ር አሥራት ዓፀደወይን Asrat Atsedeweyn መጽሐፍ በጎንደር ከተማ እየተመረቀ ነው።
ይህ መጽሐፍ መታሰቢያነቱ ስጎንደር ዩኒቨርሲቲ ርስታቸወነ ስሰጡ 59 የጎንደር አርሶ አደሮች፧ እንዲሁም በተለያዩ ዘመናት በአመራርነት፤ በባለሙያነት፤ በሠራተኛነትና በአጋርነት አገልግለው ተቋሙን አሁን ላስበት ታላቅ ደረጃ ኣደረሱ ሞስንነ ባለውለታዎች በሙሉ ይሁን፡፡
***
ከመጽሐፉ ጀርባ (blurb)
ጎንደር የኒቨርሲቲ ኢትዮጵያ ካፈራቻቸው ዩኒቨርሲቲዎች በአንጋፋነት ተርታ የሚመደብ ነው:: በቅርቡም ሰባኛ ዓመቱንና የዩኒቨርሲቲው አስኳል የሆነውን ሆስፒታሉን መቶኛ ዓመት በደማቅ ሁኔታ መዘከሩ ይታወሳል። በዚህ የታሪክ አጋጣሚ የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት የሆነው ዶ/ር አሥራት ዓፀደወይን እነሆ የዩኒቨርሲቲውን ታሪካዊ ጉዞ እርሱ ራሱ በተለያዩ የኃላፊነት እርከኖች ካከናወናቸው ተግባራት ጋር አዛምዶ የሚዘግብ፣ በጠንካራ መረጃ ላይ የተዋቀረ መጽሐፍ አቅርቦልናል።
በዚህም የዩኒቨርሲቲ ቆይታቸውን ከግለ ታሪካቸው ጋር አሰናስለው ለንባብ ያበቁትን የቀደምት የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንቶችን ፈለግ ተከትሏል ማለት ይቻላል። የተቋሙ ታሪካዊ ጉዞ በስኬት የታጀበውን ያህል አያሌ ፈተዎችና ተግዳሮቶችም የተጋረጡበት ነበር። የመጽሐፉ ትልቁ ፋይዳም እነዚህን ስኬቶችና ተግዳሮቶች ነቅሶ በማውጣት ሰፊ ግንዛቤ መስጠቱ ላይ ነው:: በተለይም በደራሲው አመራር የተከናወኑትን P70/100 ዝክረ በዓል ዘርፈ ብዙ ዝግጅቶችና ክንዋኔዎች በዝርዝር ያትታል፤ ዘላቂ እርባናቸውንም ይጠቁማል። በመጨረሻም ከዩኒቨርሲቲ አመራር ተሞክሮው የቀሰማቸውን ትምህርቶች በተመሳሳይ ተቋም ግንባታ ላይ ላሉ ያካፍላል።
ባሕሩ ዘውዴ፣ የታሪክ ኤሜሪተስ ፕሮፌሰር አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ
***
የስኬታማ ተቋማትና የአገር ግንባታ በትውልዶች ቅብብሎሽ፣ በቁርጠኝነትና በመሪዎች እቅድ ላይይመረኮዛል። ዶ/ር አሥራት ዓፀደወይን በዚህ መጽሐፋቸው የጎንደር ዩኒቨርሲቲን የ7ዐ ዓመታት ጉዞ፣ በየዘመናቱ የነበሩ መሪዎችንና ባለድርሻ አካላትን አበርክቶ፣ እንዲሁም የራሳቸውን የኃላፊነት ዘመን ፈተናና ስኬት በጥልቀት አቅርበዋል። በከፍተኛ ትምህርት አመራርነት በነበረኝ የረጅም ጊዜ ኃላፊነት ተቋሙንም ሆነ ደራሲውን በቅርብ እንደማወቄ መጠን፤ ይህ መጽሐፍ ከተጨባጩ ዓለም የተገኘ ጥልቅ እውቀት የሚሰጥ፣ ለመሰል ተቋማት መሪዎችና ተመራማሪዎች ታላቅ ማስተማሪያና ማጣቀሻ እንደሚሆን ሙሉ እምነት አለኝ።
ሳሙኤል ክፍሌ (ዶ/ር)፣ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ኘሬዚደንት
***
ጎንደር ዩኒቨርሲቲ በፈተናዎች ውስጥ ያለፈ ታላቅ ዓለም አቀፍ ተቋም ቢሆንም፣ የነበረው የታሪክ ምዝገባ ግን በቂ አልነበረም:: የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ዶ/ር አሥራት ዓፀደወይን “ጽናት” በተሰኘው መጽሐፋቸው ይህንን የታሪክ ክፍተት ለመሙላት ሞክረዋል። መጽሐፉ፣ ተቋሙ በፈተናዎች ውስጥ አልፎ ለዛሬው ስኬት እንዲበቃ አሻራቸውን ያሳረፉ የቀድሞ ከፍተኛ አመራሮችን እውቅና ይሰጣል። በተጨማሪም፣ ዶ/ር አሥራት ላለፉት ስምንት ዓመታት በኘሬዚዳንትነት ሲያገለግሉ ያጋጠሟቸውን ከባድ ፈተናዎች እንዴት በብቃት እንደተወጧቸውና የዩኒቨርሲቲውን ስኬት እንዴት ማስቀጠል እንደቻሉ ያሳያል። ይህም ለተቋሙ ቀጣይ ጤናማ የአመራር ሽግግርና ለተተኪ አመራሮች ትልቅ ስንቅ የሚሆን ነው።
ዶ/ር ደሳለኝ መንገሻ፣ በኦሃዮ ስቴት ግሎባል ዋን ሄልዝ የኢትዮጵያ ዳይሬክተር እና የቀድሞ የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት
እንኳን ደስ አለህ!
12 days ago
ለአፍሪካውያን ታዳጊዎች የህልም ምሳሌ የሆኑት ጥቋቁር ወርቆች መድመቃቸውን ቀጥለዋል።
*ከጎዳና ህይወት እስከ አለም አቀፍ መድረክ
*አስከፊ ከሆነ የጎዳና ህይወት ተነስተው ከዝነኛዋ ሻኪራ ጋር እስከ መጣመር የደረሱት ጥቋቁር የአፍሪካ ወርቆች
#ethiopia | በምስራቅ አፍሪካ የጥበብ ዓለም ውስጥ የብዙዎችን ቀልብ የሳቡት የኡጋንዳው የዳንስ ቡድን ጌቶ ኪድስ የችሎታ እና የጽናት ተምሳሌት በመሆን ዓለምን እያስደነቁ ይገኛሉ።
ቡድኑ የተመሰረተው በኡጋንዳዋ ካምፓላ ከተማ በሚገኘው የካታዌ (Katwe) ሰፈር ነው።
በዳውዳ ካቫማ አማካኝነት የተደራጁት እነዚህ ታዳጊዎች መነሻቸው ከምንም ነበር ማለት ይቻላል።
እነዚህ ህጻናት በተስፋ መቁረጥ ውስጥ የነበሩ ከድህነት ጋር በጎዳና ህይወት ላይ የነበሩ ናቸው።
ይህ ብልሁ ዳውዳ ካቫማ የተባለው ወጣት ታዳጊዎችን በመሰብሰብ በሙዚቃ እና በዳንስ ተስፋ እንዲሰንቁ ብሎም ስማቸውን አለም እንዲያውቀው አድርጓል።
የዳውዳ ካቫማ አላማ የነበረው መዝናኛን ብቻ ሳይሆን ችሎታን በመጠቀም የጎዳና ላይ ህይወት በአማራጭ መንገድ ሊቀየር እንደሚችል ለዓለም ማሳየት ነበር።
ቡድኑ መጀመሪያ ላይ ትኩረት ያደረገው ጎዳና ላይ በመጨፈር የነበረ ሲሆን የነበራቸው ጉልበት እና ተፈጥሯዊ የዳንስ ችሎታ በየማህበራዊ ሚዲያው በወጡ አጫጭር ቪዲዮዎች የዓለምን ትኩረት በቶሎ እንዲስቡ አድርጓቸዋል።
ጌቶ ኪድስ ከኡጋንዳ አልፈው ዓለም አቀፍ እውቅና ያገኙት በተለያዩ የዓለም የሙዚቃ ቪዲዮዎች ላይ በመሳተፍ ነው።
በተለይም በፈረንጆቹ 2017 ላይ ከፈረንሳዊው አርቲስት ፍሬንች ሞንታና (French Montana) ጋር በሰሩት "Unforgettable" የሙዚቃ ቪዲዮ አማካኝነት ስማቸው በዓለም አቀፍ ደረጃ በሰፊው ተሰማ።
ጌቶ ኪድስ በዓለም አቀፍ ደረጃ በታላላቅ የሙዚቃ ሽልማቶች ላይ ተጋባዥ ሆነዋል።
በዓለም አቀፍ የቴሌቪዥን ፕሮግራሞች ላይ በመቅረብ የኡጋንዳን እና የአፍሪካን ስም በከፍተኛ ደረጃ እያስጠሩም ይገኛሉ።
በቅርቡ በተጠናቀቀው የ2026 የዓለም ዋንጫ የፍጻሜ ጨዋታ ላይ ከዝነኛዋ ሻኪራ ጋር በመጣመር ባሳዩት ብቃት የስኬት ጉዟቸውን ከፍታ ላይ አድርሰውታል።
ዛሬ "ጌቶ ኪድስ" የዳንስ ቡድን ብቻ ሳይሆን የበርካታ አፍሪካውያን ታዳጊዎች የህልም ምሳሌ ሆነዋል።
ሔኖክ ወ/ገብርኤል
#ethiopia #getutemesgen #getunews #ugandaghettokids #dancingwithshakira #worldcupfinal
*ከጎዳና ህይወት እስከ አለም አቀፍ መድረክ
*አስከፊ ከሆነ የጎዳና ህይወት ተነስተው ከዝነኛዋ ሻኪራ ጋር እስከ መጣመር የደረሱት ጥቋቁር የአፍሪካ ወርቆች
#ethiopia | በምስራቅ አፍሪካ የጥበብ ዓለም ውስጥ የብዙዎችን ቀልብ የሳቡት የኡጋንዳው የዳንስ ቡድን ጌቶ ኪድስ የችሎታ እና የጽናት ተምሳሌት በመሆን ዓለምን እያስደነቁ ይገኛሉ።
ቡድኑ የተመሰረተው በኡጋንዳዋ ካምፓላ ከተማ በሚገኘው የካታዌ (Katwe) ሰፈር ነው።
በዳውዳ ካቫማ አማካኝነት የተደራጁት እነዚህ ታዳጊዎች መነሻቸው ከምንም ነበር ማለት ይቻላል።
እነዚህ ህጻናት በተስፋ መቁረጥ ውስጥ የነበሩ ከድህነት ጋር በጎዳና ህይወት ላይ የነበሩ ናቸው።
ይህ ብልሁ ዳውዳ ካቫማ የተባለው ወጣት ታዳጊዎችን በመሰብሰብ በሙዚቃ እና በዳንስ ተስፋ እንዲሰንቁ ብሎም ስማቸውን አለም እንዲያውቀው አድርጓል።
የዳውዳ ካቫማ አላማ የነበረው መዝናኛን ብቻ ሳይሆን ችሎታን በመጠቀም የጎዳና ላይ ህይወት በአማራጭ መንገድ ሊቀየር እንደሚችል ለዓለም ማሳየት ነበር።
ቡድኑ መጀመሪያ ላይ ትኩረት ያደረገው ጎዳና ላይ በመጨፈር የነበረ ሲሆን የነበራቸው ጉልበት እና ተፈጥሯዊ የዳንስ ችሎታ በየማህበራዊ ሚዲያው በወጡ አጫጭር ቪዲዮዎች የዓለምን ትኩረት በቶሎ እንዲስቡ አድርጓቸዋል።
ጌቶ ኪድስ ከኡጋንዳ አልፈው ዓለም አቀፍ እውቅና ያገኙት በተለያዩ የዓለም የሙዚቃ ቪዲዮዎች ላይ በመሳተፍ ነው።
በተለይም በፈረንጆቹ 2017 ላይ ከፈረንሳዊው አርቲስት ፍሬንች ሞንታና (French Montana) ጋር በሰሩት "Unforgettable" የሙዚቃ ቪዲዮ አማካኝነት ስማቸው በዓለም አቀፍ ደረጃ በሰፊው ተሰማ።
ጌቶ ኪድስ በዓለም አቀፍ ደረጃ በታላላቅ የሙዚቃ ሽልማቶች ላይ ተጋባዥ ሆነዋል።
በዓለም አቀፍ የቴሌቪዥን ፕሮግራሞች ላይ በመቅረብ የኡጋንዳን እና የአፍሪካን ስም በከፍተኛ ደረጃ እያስጠሩም ይገኛሉ።
በቅርቡ በተጠናቀቀው የ2026 የዓለም ዋንጫ የፍጻሜ ጨዋታ ላይ ከዝነኛዋ ሻኪራ ጋር በመጣመር ባሳዩት ብቃት የስኬት ጉዟቸውን ከፍታ ላይ አድርሰውታል።
ዛሬ "ጌቶ ኪድስ" የዳንስ ቡድን ብቻ ሳይሆን የበርካታ አፍሪካውያን ታዳጊዎች የህልም ምሳሌ ሆነዋል።
ሔኖክ ወ/ገብርኤል
#ethiopia #getutemesgen #getunews #ugandaghettokids #dancingwithshakira #worldcupfinal
12 days ago
አረንጓዴ አሻራ ለታችኞቹ የናይል ተፋሰስ ሀገራት ያለው ፋይዳ
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 17፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ዓለማችንን በአሁኑ ወቅት እየፈተኑ ከሚገኙ ጉዳዮች መካከል የአየር ንብረት ለውጥ ያስከተላቸው ጫናዎች በቀዳሚነት ይጠቀሳሉ።
የአየር ንብረት ለውጥ በሚያስከትላቸው ቀውሶች በእጅጉ ከሚፈተኑት የተፈጥሮ ሀብቶች መካከል ውሃ ቀዳሚውን ስፍራ ይይዛል።
በድርቅም ሆነ በጎርፍ እንዲሁም የገጸ ምድር ውሃ በደለል መሞላት በዘላቂነት የውሃ ልማትን ለማረጋገጥ የሚደረገውን ጥረት ያደናቅፋል።
በመሆኑም ኢትዮጵያ ውሃን ጨምሮ ለተፈጥሮ ሃብት የአየር ንብረት ለውጥ ተጋላጭነት ምላሽ ለመስጠት ተግባራዊ ርምጃ በመውሰድ የተለያዩ ተግባራትን እያከናወነች ትገኛለች።
ከእነዚህ ተግባራት መካከል ተጨባጭ ለውጥ እያስመዘገበ የሚገኘው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር ሲሆን፤ በመርሐ ግብሩ ስኬት ኢትዮጵያ በዓለም መድረክ ስሟ በጉልህ እንዲጠቀስ አድርጓል።
በመንግሥት ቆራጥነት እየተተገበረ ያለው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር የኢትዮጵያውያንን ልብና ጉልበት በአንድነት ያስተሳሰረ ታላቅ ሀገራዊ ተግባር ሆኖ ቀጥሏል።
ይህ በ2011 ዓ.ም በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀሳብ አመንጪነት በይፋ የተጀመረው መርሐ ግብር ዛፍ ከመትከል ባሻገር ውሃን ጨምሮ ለተፈጥሮ ሀብቶቻችን ዋስትና የሰጠ ውጤት አስመዝግቧል።
መንግሥት ለመርሐ ግብሩ ከፍተኛ ትኩረት በመስጠት በባለቤትነት በመምራትና ህዝቡም ጥሪውን ተቀብሎ በነቂስ በመውጣት ላለፉት ዓመታት ያሳዩት ቁርጠኝነት የሀገሪቱን ደን ሽፋን ወደ አዲስ ምዕራፍ አሸጋግሮታል።
በአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር እስከ 2017 ዓ.ም ድረስ ብቻ ከ48 ቢሊየን በላይ ችግኞች ተተክለዋል። ከዚህ ውስጥ 18 ነጥብ 7 ቢሊየኑ በዓባይ ተፋሰስ ላይ ብቻ የተተከለ ነው።
ይህም 40 በመቶ ድርሻ እንዳለው ያሳያል፥ ሆኖም ኢትዮጵያ በዓባይ ተፋሰስ ውሃውን መጠቀም ብቻ ሳይሆን የመንከባከብ ስራም እየሠራች ማለት ያስችላል።
በዚህም የታችኛው ተፋሰስ ሀገራት በደን መራቆት ምክንያት የሚከሰት ድንገተኛ የጎርፍ አደጋ ስጋታቸው ይቀረፋል። በተጨማሪም ዓመቱን ሙሉ አስተማማኝ የሆነ የውሃ ፍሰት ተጠቃሚ ይሆናሉ።
በዓባይ ተፋሰስ ላይ የተከናወነው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ችግኝ ተከላ በወንዞች ላይ የሚፈጠረው ደለል እንዲቀንስ እና በወንዞች ላይ ይከማች የነበረውን ከፍተኛ ደለል እንዲቀንስ በማድረግ ለውሃ ሀብት ጥበቃ ትልቅ አስተዋጽዖ እያበረከተ ይገኛል።
አረንጓዴ ዐሻራ ከላይ ከተጠቀሱት ጥቅሞች በተጨማሪ ለዘላቂ የውሃ ሀብት ጥበቃ በርካታ አስተዋጽኦ እያበረከተ እንደሚገኝ ማየት ይቻላል።
ደን ማልማት የዝናብ ውሃ ወደ መሬት ውስጥ እንዲሰርግ በማድረግ የውሃ ምንጮችን ያጠናክራል፣ የአፈር መሸርሸርን ይቀንሳል፣ የዛፍ ሥር አፈርን በማቆየት ወደ ውሃ አካላት የሚደርሰውን ደለል ይቀንሳል።
ይህም የውሃ ጥራት ይጠብቃል፣ የጎርፍ አደጋ ይቀንሳል።
ደን ድንገተኛ ጎርፍን ስለሚቀንስ የውሃ አካላት በዘላቂነት ያገለግላሉ፤ ዝናብን በማመጣጠን የውሃ ሀብት ቀጣይነት ያለው እንዲሆን ያግዛል።
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 17፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ዓለማችንን በአሁኑ ወቅት እየፈተኑ ከሚገኙ ጉዳዮች መካከል የአየር ንብረት ለውጥ ያስከተላቸው ጫናዎች በቀዳሚነት ይጠቀሳሉ።
የአየር ንብረት ለውጥ በሚያስከትላቸው ቀውሶች በእጅጉ ከሚፈተኑት የተፈጥሮ ሀብቶች መካከል ውሃ ቀዳሚውን ስፍራ ይይዛል።
በድርቅም ሆነ በጎርፍ እንዲሁም የገጸ ምድር ውሃ በደለል መሞላት በዘላቂነት የውሃ ልማትን ለማረጋገጥ የሚደረገውን ጥረት ያደናቅፋል።
በመሆኑም ኢትዮጵያ ውሃን ጨምሮ ለተፈጥሮ ሃብት የአየር ንብረት ለውጥ ተጋላጭነት ምላሽ ለመስጠት ተግባራዊ ርምጃ በመውሰድ የተለያዩ ተግባራትን እያከናወነች ትገኛለች።
ከእነዚህ ተግባራት መካከል ተጨባጭ ለውጥ እያስመዘገበ የሚገኘው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር ሲሆን፤ በመርሐ ግብሩ ስኬት ኢትዮጵያ በዓለም መድረክ ስሟ በጉልህ እንዲጠቀስ አድርጓል።
በመንግሥት ቆራጥነት እየተተገበረ ያለው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር የኢትዮጵያውያንን ልብና ጉልበት በአንድነት ያስተሳሰረ ታላቅ ሀገራዊ ተግባር ሆኖ ቀጥሏል።
ይህ በ2011 ዓ.ም በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀሳብ አመንጪነት በይፋ የተጀመረው መርሐ ግብር ዛፍ ከመትከል ባሻገር ውሃን ጨምሮ ለተፈጥሮ ሀብቶቻችን ዋስትና የሰጠ ውጤት አስመዝግቧል።
መንግሥት ለመርሐ ግብሩ ከፍተኛ ትኩረት በመስጠት በባለቤትነት በመምራትና ህዝቡም ጥሪውን ተቀብሎ በነቂስ በመውጣት ላለፉት ዓመታት ያሳዩት ቁርጠኝነት የሀገሪቱን ደን ሽፋን ወደ አዲስ ምዕራፍ አሸጋግሮታል።
በአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር እስከ 2017 ዓ.ም ድረስ ብቻ ከ48 ቢሊየን በላይ ችግኞች ተተክለዋል። ከዚህ ውስጥ 18 ነጥብ 7 ቢሊየኑ በዓባይ ተፋሰስ ላይ ብቻ የተተከለ ነው።
ይህም 40 በመቶ ድርሻ እንዳለው ያሳያል፥ ሆኖም ኢትዮጵያ በዓባይ ተፋሰስ ውሃውን መጠቀም ብቻ ሳይሆን የመንከባከብ ስራም እየሠራች ማለት ያስችላል።
በዚህም የታችኛው ተፋሰስ ሀገራት በደን መራቆት ምክንያት የሚከሰት ድንገተኛ የጎርፍ አደጋ ስጋታቸው ይቀረፋል። በተጨማሪም ዓመቱን ሙሉ አስተማማኝ የሆነ የውሃ ፍሰት ተጠቃሚ ይሆናሉ።
በዓባይ ተፋሰስ ላይ የተከናወነው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ችግኝ ተከላ በወንዞች ላይ የሚፈጠረው ደለል እንዲቀንስ እና በወንዞች ላይ ይከማች የነበረውን ከፍተኛ ደለል እንዲቀንስ በማድረግ ለውሃ ሀብት ጥበቃ ትልቅ አስተዋጽዖ እያበረከተ ይገኛል።
አረንጓዴ ዐሻራ ከላይ ከተጠቀሱት ጥቅሞች በተጨማሪ ለዘላቂ የውሃ ሀብት ጥበቃ በርካታ አስተዋጽኦ እያበረከተ እንደሚገኝ ማየት ይቻላል።
ደን ማልማት የዝናብ ውሃ ወደ መሬት ውስጥ እንዲሰርግ በማድረግ የውሃ ምንጮችን ያጠናክራል፣ የአፈር መሸርሸርን ይቀንሳል፣ የዛፍ ሥር አፈርን በማቆየት ወደ ውሃ አካላት የሚደርሰውን ደለል ይቀንሳል።
ይህም የውሃ ጥራት ይጠብቃል፣ የጎርፍ አደጋ ይቀንሳል።
ደን ድንገተኛ ጎርፍን ስለሚቀንስ የውሃ አካላት በዘላቂነት ያገለግላሉ፤ ዝናብን በማመጣጠን የውሃ ሀብት ቀጣይነት ያለው እንዲሆን ያግዛል።
13 days ago
የወደፊትን ዛሬ የሚገነባ መሪና አመራር፤ ዶ/ር ረሻድ ከማል
Mujib Amino
#ethiopia | የማንኛውም የልማት ተቋም ስኬት የሚለካው በሚገነባቸው ፕሮጀክቶች ብዛት ብቻ አይደለም፤ ተቋሙ የሚገነባው ተቋማዊ አቅም፣ የሚያዳብረው የአመራር ባህል፣ የሚፈጥረው የሰው ኃይል ብቃት እና ለህብረተሰቡ የሚያመጣው ዘላቂ ጥቅምም ነው። በዚህ መለኪያ መሠረት፣ የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን ባለፉት ዓመታት ያከናወነው የተቋማዊ ለውጥ ከተለያዩ ግዙፍ ሀገር በቀል ተቋማት ውስጥ ሊጠቀስ የሚችል ወርቃማ ሂደት ነው።
የኮርፖሬሽኑ የ2018 በጀት ዓመት የሥራ አፈጻጸም ግምገማና የ2019 በጀት ዓመት እቅድ መድረክ የዓመታዊ ሪፖርት ማቅረቢያ ብቻ አይደለም፤ ያለፈውን በማጠናከር የወደፊቱን በማቀድ የሚጓዝ የአመራር ባህል መገለጫ ነው። እቅድን ማውጣት፣ አፈጻጸሙን መለካት፣ ጉድለቶችን መለየትና እንደገና ማሻሻል የሚችል ተቋም የረጅም ጊዜ ውጤት የማስመዝገብ አቅም ያለው መሆኑን ያሳያል።
በዚህ ሂደት ዶ/ር ረሻድ ከማል ያሳዩት የአመራር አቅጣጫ ተቋሙን ከዕለታዊ የሥራ እንቅስቃሴ በላይ ወደ ራዕይ ተኮር አመራር ለማሸጋገር የታሰበ መሆኑን ከቀረቡት መግለጫዎች መረዳት ይቻላል።
የተቋማት ስኬት የአንድ ግለሰብ ስኬት ሳይሆን የራዕይ፣ የቁርጠኝነት፣ የቡድን ሥራ እና የመንግሥት ድጋፍ ውጤት ነው። የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን ባለፉት ዓመታት ያሳየው የለውጥ ጉዞ፣ የሪፎርም አተገባበር፣ የእቅድ ተኮር አመራር እና የወደፊት የቤት ልማት ራዕይ በቀጣይነት ሊጠናከር የሚገባው ተቋማዊ አቅጣጫ መሆኑን ያመለክታል።
ከዚህ አንፃር፣ የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ዶ/ር ረሻድ ከማል እየመሩት ያለው የለውጥ ጉዞ እና የተቋማዊ ሪፎርም እንቅስቃሴ የተገኙትን ውጤቶች በተጨባጭ መለኪያዎች እየተገመገመ የሚቀጥል ከሆነ፣ መንግሥትም እንዲህ ዓይነቱን የተቋማዊ አመራር ማበረታታት፣ አስፈላጊውን የፖሊሲና የተቋማዊ ድጋፍ መስጠት፣ እንዲሁም ለተመዘገቡ ውጤቶች ተገቢ እውቅና መስጠት ለሌሎች የህዝብ ተቋማትም አበረታች ምሳሌ ሊሆን ይችላል።
ስኬታማ የተቋማዊ ሪፎርም እና የልማት አመራር በቀጣይነት እንዲጠናከር የሚያስፈልገው ሽልማት ብቻ ሳይሆን፣ የበለጠ የሥራ ነፃነት፣ ተቋማዊ ድጋፍ፣ የፋይናንስ አቅም እና ለረጅም ጊዜ ዕቅዶች የሚያስፈልጉ ምቹ ሁኔታዎች መፍጠር ነው። ይህ ሲሆን የተቋሙ የወደፊት የቤት ልማት ራዕይ በተሻለ ሁኔታ ወደ ተግባር የመቀየር እድሉ ይጨምራል።
በመሆኑም የለውጥ አመራሮችን በተጨባጭ ውጤታቸው መሠረት ማበረታታት፣ እውቅና መስጠት እና የበለጠ የመስራት እድል መፍጠር የአንድ ግለሰብን ስኬት ከማጎልበት በላይ በመላው የህዝብ አገልግሎት ሥርዓት ውስጥ የውጤት፣ የተጠያቂነት እና የላቀ አፈፃፀም ባህልን ለማጠናከር ያስችላል። ይህ ደግሞ በመጨረሻ ተጠቃሚው ህዝብ የተሻለ አገልግሎት እንዲያገኝ እና የሀገሪቱ የልማት ግቦች በተሻለ ፍጥነት እንዲሳኩ አስተዋጽኦ ያበረክታል።
የተቋማዊ ሪፎርም ማዕከል
በኮርፖሬሽኑ የተተገበረው የሪፎርም ሥራ ከፍተኛ ውጤት አስመዝግበዋል፣ የለውጥ ፕሮግራሞች በሰነድ ላይ ብቻ የቀሩ ሳይሆን ወደ አሠራር እንዲወርዱ ጥረት መደረጉን ያሳያል። በዘመናዊ የህዝብ ተቋማት አመራር ውስጥ የሪፎርም ትርጉም የሥራ ፍጥነትን ማሳደግ፣ የተጠያቂነት ሥርዓትን ማጠናከር፣ የአገልግሎት ጥራትን ማሻሻል እና ለውጤት ቅድሚያ መስጠት ነው።
የፋይናንስ ጥንካሬ እና ዘላቂነት
የተቋሙን ገቢ ማሳደግ፣ የሀብት አስተዳደርን ማጠናከር እና ለቀጣይ ፕሮጀክቶች የሚያስፈልገውን የፋይናንስ መሠረት መፍጠር በማንኛውም የልማት ተቋም ውስጥ ወሳኝ ጉዳይ ነው። በዚህም ረገድ ትኩረት መደረጉ ግልፅ ነዉ፤ ይህም የረጅም ጊዜ ዕቅዶችን ለማስፈጸም አስፈላጊ መሠረት ነው።
የሰው ሀብት፤ የለውጥ ዋና ኃይል
ተቋማት የሚቀየሩት በሰዎች ነው። ስለዚህ ሰራተኞችን ማብቃት፣ የትብብር ባህልን ማጎልበት፣ የውጤት ተኮር አስተሳሰብን ማስረጽ እና ቀጣይ ትውልድ መሪዎችን ማፍራት ዘላቂ ለውጥ የሚያመጡ መሠረታዊ ጉዳዮች ናቸው።
ዘመናዊ አሠራርና ተወዳዳሪነት
የዘመናዊ አሠራር ሥርዓት ማለት የቴክኖሎጂ አጠቃቀም ብቻ ሳይሆን፣ የውሳኔ አሰጣጥን ማፋጠን፣ የመረጃ ፍሰትን ማሻሻል፣ የአገልግሎት ጥራትን ማሳደግ እና የተቋሙን የውስጥ ቅንጅት ማጠናከር ጭምር ነው። እነዚህ በረጅም ጊዜ የተቋሙን ተወዳዳሪነት ሊያጠናክሩ ይችላሉ።
50 ዓመታትን ወደ አዲስ ምዕራፍ
“በአዲስ ምዕራፍ ለተሻለ ነገ” በሚል መሪ ሃሳብ የተከበረው የ50ኛ ዓመት የወርቅ ኢዮቤልዩ በዓል ያለፈውን በማክበር ብቻ ሳይሆን ለወደፊቱ የተሻለ አቅጣጫ ለመቅረጽ የተጠቀመበት አጋጣሚ ነበር። ከጥንካሬዎች ቀጣይነት መውሰድና ከክፍተቶች መማር የሚለው መርህ የተሻለ ተቋማዊ ባህልን ያመለክታል።
የቤት አቅርቦት፤ የተቋሙ ዋና ተልዕኮ
“የቤት አቅርቦት ፍላጎትን በዘላቂነት ለመመለስ በትኩረት እንሰራለን” የሚለው መልዕክት የተቋሙ ራዕይ በመሠረታዊ የህዝብ ፍላጎት ላይ የተመሰረተ መሆኑን ያሳያል። የመኖሪያ ቤት ችግር የከተማ ልማት፣ የኢኮኖሚ እድገት እና የማህበራዊ መረጋጋት ጋር በቀጥታ የተያያዘ ስለሆነ፣ በዚህ ዘርፍ ዘላቂ መፍትሄ ማፈላለግ የረጅም ጊዜ የልማት ራዕይን ያሳያል።
የትብብር አመራር
የመኖሪያ ቤት አቅርቦት ከመንግሥት፣ ከግሉ ዘርፍ፣ ከፋይናንስ ተቋማትና ከሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር በቅርብ ትብብር የሚሰራ ዘርፍ ነው። ስለዚህ የተጠቀሰው የአጋርነት ጥሪ የተቋሙን ችግሮች በጋራ የመፍታት አቅጣጫ ያንጸባርቃል።
የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን የተቋማዊ ለውጥ ጉዞ የሪፎርም፣ የእቅድ ተኮር አመራር፣ የሰው ኃይል ልማት እና የረጅም ጊዜ የቤት አቅርቦት ራዕይ ላይ ያተኮረ መሆኑን ያመለክታል። ተቋሙ የ2018 አፈጻጸምን በመገምገም እና የ2019 እቅዱን በማዘጋጀት የሚያሳየው አካሄድ፣ የተቋማዊ መሻሻል ሂደት በቀጣይነት እንዲቀጥል የሚያግዝ መሠረት መሆኑን ያሳያል።
Abiy Ahmed Ali
Federal Housing Corporation - Ethiopia
Worku Gachena-ወርቁ ጋቸና
Mujib Amino
#ethiopia | የማንኛውም የልማት ተቋም ስኬት የሚለካው በሚገነባቸው ፕሮጀክቶች ብዛት ብቻ አይደለም፤ ተቋሙ የሚገነባው ተቋማዊ አቅም፣ የሚያዳብረው የአመራር ባህል፣ የሚፈጥረው የሰው ኃይል ብቃት እና ለህብረተሰቡ የሚያመጣው ዘላቂ ጥቅምም ነው። በዚህ መለኪያ መሠረት፣ የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን ባለፉት ዓመታት ያከናወነው የተቋማዊ ለውጥ ከተለያዩ ግዙፍ ሀገር በቀል ተቋማት ውስጥ ሊጠቀስ የሚችል ወርቃማ ሂደት ነው።
የኮርፖሬሽኑ የ2018 በጀት ዓመት የሥራ አፈጻጸም ግምገማና የ2019 በጀት ዓመት እቅድ መድረክ የዓመታዊ ሪፖርት ማቅረቢያ ብቻ አይደለም፤ ያለፈውን በማጠናከር የወደፊቱን በማቀድ የሚጓዝ የአመራር ባህል መገለጫ ነው። እቅድን ማውጣት፣ አፈጻጸሙን መለካት፣ ጉድለቶችን መለየትና እንደገና ማሻሻል የሚችል ተቋም የረጅም ጊዜ ውጤት የማስመዝገብ አቅም ያለው መሆኑን ያሳያል።
በዚህ ሂደት ዶ/ር ረሻድ ከማል ያሳዩት የአመራር አቅጣጫ ተቋሙን ከዕለታዊ የሥራ እንቅስቃሴ በላይ ወደ ራዕይ ተኮር አመራር ለማሸጋገር የታሰበ መሆኑን ከቀረቡት መግለጫዎች መረዳት ይቻላል።
የተቋማት ስኬት የአንድ ግለሰብ ስኬት ሳይሆን የራዕይ፣ የቁርጠኝነት፣ የቡድን ሥራ እና የመንግሥት ድጋፍ ውጤት ነው። የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን ባለፉት ዓመታት ያሳየው የለውጥ ጉዞ፣ የሪፎርም አተገባበር፣ የእቅድ ተኮር አመራር እና የወደፊት የቤት ልማት ራዕይ በቀጣይነት ሊጠናከር የሚገባው ተቋማዊ አቅጣጫ መሆኑን ያመለክታል።
ከዚህ አንፃር፣ የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ዶ/ር ረሻድ ከማል እየመሩት ያለው የለውጥ ጉዞ እና የተቋማዊ ሪፎርም እንቅስቃሴ የተገኙትን ውጤቶች በተጨባጭ መለኪያዎች እየተገመገመ የሚቀጥል ከሆነ፣ መንግሥትም እንዲህ ዓይነቱን የተቋማዊ አመራር ማበረታታት፣ አስፈላጊውን የፖሊሲና የተቋማዊ ድጋፍ መስጠት፣ እንዲሁም ለተመዘገቡ ውጤቶች ተገቢ እውቅና መስጠት ለሌሎች የህዝብ ተቋማትም አበረታች ምሳሌ ሊሆን ይችላል።
ስኬታማ የተቋማዊ ሪፎርም እና የልማት አመራር በቀጣይነት እንዲጠናከር የሚያስፈልገው ሽልማት ብቻ ሳይሆን፣ የበለጠ የሥራ ነፃነት፣ ተቋማዊ ድጋፍ፣ የፋይናንስ አቅም እና ለረጅም ጊዜ ዕቅዶች የሚያስፈልጉ ምቹ ሁኔታዎች መፍጠር ነው። ይህ ሲሆን የተቋሙ የወደፊት የቤት ልማት ራዕይ በተሻለ ሁኔታ ወደ ተግባር የመቀየር እድሉ ይጨምራል።
በመሆኑም የለውጥ አመራሮችን በተጨባጭ ውጤታቸው መሠረት ማበረታታት፣ እውቅና መስጠት እና የበለጠ የመስራት እድል መፍጠር የአንድ ግለሰብን ስኬት ከማጎልበት በላይ በመላው የህዝብ አገልግሎት ሥርዓት ውስጥ የውጤት፣ የተጠያቂነት እና የላቀ አፈፃፀም ባህልን ለማጠናከር ያስችላል። ይህ ደግሞ በመጨረሻ ተጠቃሚው ህዝብ የተሻለ አገልግሎት እንዲያገኝ እና የሀገሪቱ የልማት ግቦች በተሻለ ፍጥነት እንዲሳኩ አስተዋጽኦ ያበረክታል።
የተቋማዊ ሪፎርም ማዕከል
በኮርፖሬሽኑ የተተገበረው የሪፎርም ሥራ ከፍተኛ ውጤት አስመዝግበዋል፣ የለውጥ ፕሮግራሞች በሰነድ ላይ ብቻ የቀሩ ሳይሆን ወደ አሠራር እንዲወርዱ ጥረት መደረጉን ያሳያል። በዘመናዊ የህዝብ ተቋማት አመራር ውስጥ የሪፎርም ትርጉም የሥራ ፍጥነትን ማሳደግ፣ የተጠያቂነት ሥርዓትን ማጠናከር፣ የአገልግሎት ጥራትን ማሻሻል እና ለውጤት ቅድሚያ መስጠት ነው።
የፋይናንስ ጥንካሬ እና ዘላቂነት
የተቋሙን ገቢ ማሳደግ፣ የሀብት አስተዳደርን ማጠናከር እና ለቀጣይ ፕሮጀክቶች የሚያስፈልገውን የፋይናንስ መሠረት መፍጠር በማንኛውም የልማት ተቋም ውስጥ ወሳኝ ጉዳይ ነው። በዚህም ረገድ ትኩረት መደረጉ ግልፅ ነዉ፤ ይህም የረጅም ጊዜ ዕቅዶችን ለማስፈጸም አስፈላጊ መሠረት ነው።
የሰው ሀብት፤ የለውጥ ዋና ኃይል
ተቋማት የሚቀየሩት በሰዎች ነው። ስለዚህ ሰራተኞችን ማብቃት፣ የትብብር ባህልን ማጎልበት፣ የውጤት ተኮር አስተሳሰብን ማስረጽ እና ቀጣይ ትውልድ መሪዎችን ማፍራት ዘላቂ ለውጥ የሚያመጡ መሠረታዊ ጉዳዮች ናቸው።
ዘመናዊ አሠራርና ተወዳዳሪነት
የዘመናዊ አሠራር ሥርዓት ማለት የቴክኖሎጂ አጠቃቀም ብቻ ሳይሆን፣ የውሳኔ አሰጣጥን ማፋጠን፣ የመረጃ ፍሰትን ማሻሻል፣ የአገልግሎት ጥራትን ማሳደግ እና የተቋሙን የውስጥ ቅንጅት ማጠናከር ጭምር ነው። እነዚህ በረጅም ጊዜ የተቋሙን ተወዳዳሪነት ሊያጠናክሩ ይችላሉ።
50 ዓመታትን ወደ አዲስ ምዕራፍ
“በአዲስ ምዕራፍ ለተሻለ ነገ” በሚል መሪ ሃሳብ የተከበረው የ50ኛ ዓመት የወርቅ ኢዮቤልዩ በዓል ያለፈውን በማክበር ብቻ ሳይሆን ለወደፊቱ የተሻለ አቅጣጫ ለመቅረጽ የተጠቀመበት አጋጣሚ ነበር። ከጥንካሬዎች ቀጣይነት መውሰድና ከክፍተቶች መማር የሚለው መርህ የተሻለ ተቋማዊ ባህልን ያመለክታል።
የቤት አቅርቦት፤ የተቋሙ ዋና ተልዕኮ
“የቤት አቅርቦት ፍላጎትን በዘላቂነት ለመመለስ በትኩረት እንሰራለን” የሚለው መልዕክት የተቋሙ ራዕይ በመሠረታዊ የህዝብ ፍላጎት ላይ የተመሰረተ መሆኑን ያሳያል። የመኖሪያ ቤት ችግር የከተማ ልማት፣ የኢኮኖሚ እድገት እና የማህበራዊ መረጋጋት ጋር በቀጥታ የተያያዘ ስለሆነ፣ በዚህ ዘርፍ ዘላቂ መፍትሄ ማፈላለግ የረጅም ጊዜ የልማት ራዕይን ያሳያል።
የትብብር አመራር
የመኖሪያ ቤት አቅርቦት ከመንግሥት፣ ከግሉ ዘርፍ፣ ከፋይናንስ ተቋማትና ከሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር በቅርብ ትብብር የሚሰራ ዘርፍ ነው። ስለዚህ የተጠቀሰው የአጋርነት ጥሪ የተቋሙን ችግሮች በጋራ የመፍታት አቅጣጫ ያንጸባርቃል።
የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን የተቋማዊ ለውጥ ጉዞ የሪፎርም፣ የእቅድ ተኮር አመራር፣ የሰው ኃይል ልማት እና የረጅም ጊዜ የቤት አቅርቦት ራዕይ ላይ ያተኮረ መሆኑን ያመለክታል። ተቋሙ የ2018 አፈጻጸምን በመገምገም እና የ2019 እቅዱን በማዘጋጀት የሚያሳየው አካሄድ፣ የተቋማዊ መሻሻል ሂደት በቀጣይነት እንዲቀጥል የሚያግዝ መሠረት መሆኑን ያሳያል።
Abiy Ahmed Ali
Federal Housing Corporation - Ethiopia
Worku Gachena-ወርቁ ጋቸና
14 days ago
የወረቀት ሳሙናን ለገበያ ያቀረበችው የባቲ ከተማዋ ወጣት
ባቲ፣ ኢትዮጵያ — አብዛኞቻችን ሳሙናን በደረቅ (በቁራጭ)፣ በዱቄት ወይም በፈሳሽ መልክ ብቻ አውቀን ለለመድነው አጠቃቀም፣ የባቲ ከተማ ነዋሪዋ ወጣት ኢክራም ሙሐመድ አዲስና ምቹ አማራጭ ይዛ ብቅ ብላለች።
ወጣቷ ከአካባቢዋ ችግሮች በመነሳት ለእጅ መታጠቢያ የሚሆን «የወረቀት ሳሙና» በመፍጠር የብዙዎችን ትኩረት ስባለች።
ኢክራም ለዚህ የፈጠራ ሥራዋ መነሻ የሆነውን አጋጣሚ ስታብራራ፤ በተለያዩ ቦታዎች ለስራና ለጉዞ በሚንቀሳቀሱበት ወቅት እጅ ለመታጠብ የሚሆን ሳሙና ማጣት የተለመደ ፈተና በመሆኑ፣ ይህንን ክፍተት የሚሞላ መፍትሔ ለመፈለግ መነሳቷን ትናገራለች።
ይህ የወረቀት ሳሙና ከባህላዊ የሳሙና አይነቶች የሚለዩት በርካታ አዎንታዊ ጎኖች አሉት፦
* ቀደም ሲል ከምናውቃቸውና ለተላላፊ በሽታዎች ሊያጋልጡ ከሚችሉ የጋራ መጠቀሚያ ሳሙናዎች በተለየ፣ እያንዳንዱ ሰው ለብቻው በግል ለመጠቀም በሚመች መልኩ የተዘጋጀ ነው።
* በቦታ፣ በሁኔታዎችና በቦርሳ ጥበት ሳይገደቡ በየትኛውም ስፍራ ይዞ ለመንቀሳቀስ እና ለመጠቀም አጅግ ምቹ ነው።
* ከአንዱ ጥቅል ላይ አንድ ቀጭን ወረቀት በመለየት በእጅ ላይ አድርጎ በጥቂት ውሃ በማሸት ብቻ በቀላሉ መጠቀም ይቻላል።
ምርቱን ለማዘጋጀት በአካባቢዋ በቀላሉ የሚገኙ ጥሬ እቃዎችን የተጠቀመች ሲሆን፣ የእጅ ቆዳን በማይጎዳ መልኩ የኬሚካል ውህዶችን በራሷ በማቀናጀት ለወረቀት ሳሙናው የሚፈለገውን ቅርጽ አስይዛዋለች። ለዚህ ስኬቷም የአባቷ እገዛና ድጋፍ ከፍተኛ እንደነበረ ትገልጻለች።
ምርቷን በአካባቢዋ መጠሪያ «ገንደዳዩ» በሚል ስያሜ ሰይማ ወደ ገበያ ያቀረበችው ወጣት ኢክራም፤ በተለያዩ ባዛሮች ላይ በማሳተፍ ከተጠቃሚዎች እጅግ አዎንታዊ እና አበረታች ግብረ-መልስ ማግኘቷን ተናግራለች።
በቀጣይም የዚሁን የወረቀት ሳሙና ጥራትና መጠን በከፍተኛ ደረጃ በመጨመር በስፋት ለሀገር ውስጥ ገበያ ለማቅረብ ጠንክራ እየሰራች እንደሆነና የወደፊት አላማዋም ምርቱን ማስፋፋት እንደሆነ ገልጻለች።
Via አሚኮ
Seledadotio
Seledadotio
ባቲ፣ ኢትዮጵያ — አብዛኞቻችን ሳሙናን በደረቅ (በቁራጭ)፣ በዱቄት ወይም በፈሳሽ መልክ ብቻ አውቀን ለለመድነው አጠቃቀም፣ የባቲ ከተማ ነዋሪዋ ወጣት ኢክራም ሙሐመድ አዲስና ምቹ አማራጭ ይዛ ብቅ ብላለች።
ወጣቷ ከአካባቢዋ ችግሮች በመነሳት ለእጅ መታጠቢያ የሚሆን «የወረቀት ሳሙና» በመፍጠር የብዙዎችን ትኩረት ስባለች።
ኢክራም ለዚህ የፈጠራ ሥራዋ መነሻ የሆነውን አጋጣሚ ስታብራራ፤ በተለያዩ ቦታዎች ለስራና ለጉዞ በሚንቀሳቀሱበት ወቅት እጅ ለመታጠብ የሚሆን ሳሙና ማጣት የተለመደ ፈተና በመሆኑ፣ ይህንን ክፍተት የሚሞላ መፍትሔ ለመፈለግ መነሳቷን ትናገራለች።
ይህ የወረቀት ሳሙና ከባህላዊ የሳሙና አይነቶች የሚለዩት በርካታ አዎንታዊ ጎኖች አሉት፦
* ቀደም ሲል ከምናውቃቸውና ለተላላፊ በሽታዎች ሊያጋልጡ ከሚችሉ የጋራ መጠቀሚያ ሳሙናዎች በተለየ፣ እያንዳንዱ ሰው ለብቻው በግል ለመጠቀም በሚመች መልኩ የተዘጋጀ ነው።
* በቦታ፣ በሁኔታዎችና በቦርሳ ጥበት ሳይገደቡ በየትኛውም ስፍራ ይዞ ለመንቀሳቀስ እና ለመጠቀም አጅግ ምቹ ነው።
* ከአንዱ ጥቅል ላይ አንድ ቀጭን ወረቀት በመለየት በእጅ ላይ አድርጎ በጥቂት ውሃ በማሸት ብቻ በቀላሉ መጠቀም ይቻላል።
ምርቱን ለማዘጋጀት በአካባቢዋ በቀላሉ የሚገኙ ጥሬ እቃዎችን የተጠቀመች ሲሆን፣ የእጅ ቆዳን በማይጎዳ መልኩ የኬሚካል ውህዶችን በራሷ በማቀናጀት ለወረቀት ሳሙናው የሚፈለገውን ቅርጽ አስይዛዋለች። ለዚህ ስኬቷም የአባቷ እገዛና ድጋፍ ከፍተኛ እንደነበረ ትገልጻለች።
ምርቷን በአካባቢዋ መጠሪያ «ገንደዳዩ» በሚል ስያሜ ሰይማ ወደ ገበያ ያቀረበችው ወጣት ኢክራም፤ በተለያዩ ባዛሮች ላይ በማሳተፍ ከተጠቃሚዎች እጅግ አዎንታዊ እና አበረታች ግብረ-መልስ ማግኘቷን ተናግራለች።
በቀጣይም የዚሁን የወረቀት ሳሙና ጥራትና መጠን በከፍተኛ ደረጃ በመጨመር በስፋት ለሀገር ውስጥ ገበያ ለማቅረብ ጠንክራ እየሰራች እንደሆነና የወደፊት አላማዋም ምርቱን ማስፋፋት እንደሆነ ገልጻለች።
Via አሚኮ
Seledadotio
Seledadotio
17 days ago
(ዘ-ሐበሻ ስፖርት) የአንድን ቡድን ድል “የእግር ኳስ ውበት ድል” ብሎ መግለጽ ምናልባትም የተለመደና ሰልችቶን የነበረ አገላለጽ ሊመስል ይችላል። ነገር ግን በ2026ቱ የኒው ጀርሲ የዓለም ዋንጫ የፍፃሜ መድረክ ላይ ስፔን አርጀንቲናን ጥልቃ ስታሸንፍ፣ ማንኛውም ገለልተኛ የእግር ኳስ አፍቃሪ በዚህ አገላለጽ ላይ ቅሬታ ይኖረዋል ተብሎ አይታሰብም።
በጭማሪ ሰዓት ላይ ፌራን ቶሬስ ያንን ወርቃማ ግብ የአርጀንቲና መረብ ላይ ሲያሳርፈውና ሮድሪ ዋንጫውን ወደ ኒው ጀርሲ ሰማይ ከፍ አድርጎ ሲያነሳው፣ ለአርጀንቲና ብሔራዊ ቡድን ያዘነ ወይም ያነባ አንድም እውነተኛ የስፖርት አፍቃሪ አልነበረም። ስፔን የተጫዋቾችንም ሆነ የተመልካቾችን ትዕግሥት የፈተነውን ያንን አሰልቺ የአርጀንቲናውያንን የብረት መከላከያ ሰብራ በመውጣት፣ በታሪኳ ሁለተኛውን የዓለም ዋንጫ በደመቀ ሁኔታ አሳክታለች። በሁሉም የእግር ኳስ መለኪያዎች—አንዳንዶች እንደሚሉት ደግሞ በስፖርታዊ የሞራል ልዕልናም ጭምር - ይህ ፍፁም ትክክለኛና የሚገባ ውጤት ነበር።
የቀድሞው የእንግሊዝ ብሔራዊ ቡድን አጥቂ አላን ሽረር ላይ እንደተናገረው “ትክክለኛው ቡድን እንዳሸነፈ ምንም ጥርጥር የለውም። ከጅምሩ እስከ ፍፃሜው ስፔን የኳስ ቁጥጥር የበላይነቱን ወስዳለች። እግር ኳስ ለመጫወት፣ ዕድሎችን ለመፍጠርና ከተከላካይ ጀርባ ለመውጣት የሚጥሩት እነሱ ብቻ ነበሩ። ይህ ውጤት በተጫወቱበት ማራኪ መንገድ ምክንያት ለእግር ኳስ የተገኘ ትልቅ ድል ነው፤ ስፔን በእውነት ይገባታል።”
አኃዞቹ ራሳቸው እውነታውን በግልፅ ይመሰክራሉ። ስፔን 65% የኳስ ቁጥጥር፣ 1.94 የሚጠበቅ የግብ መጠን (xG) እና 20 ወደ ግብ የተደረጉ ሙከራዎችን (11ዱ ኢላማቸውን የጠበቁ) አስመዝግባለች። በአንፃሩ በሌላኛው የሜዳ ክፍል ግብ ጠባቂው ኡናይ ሲሞን በ8 ጨዋታዎች 7ኛውን ግቡን ሳያስደፍር በመውጣት የውድድሩ ምርጥ ግብ ጠባቂ በመሆን የጎልደን ግላቭ ሽልማትን አጋብሷል። ስፔን በጠቅላላው ውድድር ያስተናገደችው 1 ግብ ብቻ ሲሆን፣ ይህም በዓለም ዋንጫ ታሪክ አንድ ሻምፒዮን ቡድን ያስተናገደው አነስተኛው የግብ መጠን ሆኖ ተመዝግቧል።
የዓለም እግር ኳስን በአሁኑ ሰዓት በበላይነት እየመራ ያለው አንድ ኃይል ቢኖር እርሱም ስፔን ነው። በአሁኑ ወቅት የዓለም፣ የኦሊምፒክ እና የአውሮፓ ሻምፒዮን ናቸው - የሴቶች ቡድናቸው የዓለም ሻምፒዮን መሆኑ ሳይረሳ! የወንዶች ቡድናቸው በአሁኑ ወቅት ባደረጋቸው ያለፉት 38 ጨዋታዎች በሁሉም ውድድሮች ላይ ሽንፈት አላስተናገደም፤ ይህም በታሪክ የማንኛውም አውሮፓ ሀገር ረጅሙ ባለመሸነፍ ጉዞ ነው።
ምንም እንኳን በዚህ ውድድር መጀመሪያ ላይ ከኬፕ ቨርዴ ጋር 0ለ0 በሆነ አሰልቺ ውጤት በመጀመር አድናቂዎቻቸውን ቢያስደነግጡም፣ ልክ እንደ 2010ቱ የደቡብ አፍሪካ ዓለም ዋንጫ (በመጀመሪያው ጨዋታ በስዊዘርላንድ 1ለ0 ተሸንፈው እንደነበረው) የመክፈቻ ጨዋታቸውን ሳይያሸንፉ ቀርተው ዋንጫውን ማንሳት የቻሉበትን አስገራሚ አጋጣሚ በድጋሚ ደግመውታል።
በዓለም ዋንጫ የፍፃሜ ታሪክ ውስጥ አንድ ተጫዋች 100 እና ከዚያ በላይ ኳሶችን አቀብሎ ያጠናቀቀባቸው ሦስት አጋጣሚዎች ብቻ ሲሆኑ፣ ከእነዚህ ውስጥ ሁለቱ የተመዘገቡት በዚህ ምሽት በስፔን ተጫዋቾች ነው - ሮድሪ 101 ቅብብሎችን ሲያደርግ፣ የ19 ዓመቱ ታምረኛ ተከላካይ ፓው ኩባርሲ ደግሞ 121 ስኬታማ ቅብብሎችን አድርጓል።
ለዚህ ወጣት ቡድን ይህ ገና ጅምር ነው! ኩባርሲ የውድድሩ ምርጥ ወጣት ተጫዋች ሲባል፣ የባርሴሎና የቡድን አጋሩ ላሚን ያማል ደግሞ ገና ወደፊት ብዙ የሚያሳያቸው ወርቃማ ዓመታት ከፊቱ ይጠብቁታል። በ19 ዓመት ከ6 ቀን ዕድሜው ላሚን ያማል ከፔሌ (1958) እና ከጁሴፔ ቤርጎሚ (1982) በመቀጠል በዓለም ዋንጫ ፍፃሜ ላይ የተጫወተ ሦስተኛው ታናሽ ተጫዋች እና ሦስተኛው ታናሽ የዓለም ዋንጫ አሸናፊ መሆን ችሏል።
አርጀንቲናዎች በዓለም እግር ኳስ መድረክ ላይ ብዙ ጊዜ “ጨካኝና ተንኮለኛ” ተደርገው ይሳላሉ - በተለይም በእንግሊዝ ደጋፊዎች ዘንድ። በግማሽ ፍፃሜው ላይ በእንግሊዝ ላይ እንዳደረጉት ሁሉ፣ በዚህም ጨዋታ በመጀመሪያው አጋማሽ ላይ እግር ኳስ ለመጫወት ሳይሆን፣ የሜዳውን ውበትና የስፔንን እንቅስቃሴ ለማደናቀፍ ብቻ ትኩረት አድርገው ነበር የገቡት። ሊአንድሮ ፓሬዴስ ዋነኛው የጨዋታ አበላሺ ሲሆን፣ ኤንዞ ፈርናንዴዝ ደግሞ የእሱ ምክትል ረዳት ነበር። ምንም እንኳን አራት የአርጀንቲና ተጫዋቾች ቢጫ ካርድ ቢመለከቱም፣ ብዙዎች ግን ዳኞች ለአርጀንቲና አሁንም ቢሆን ርኅራኄ አሳይተዋል የሚል እምነት አላቸው።
አርጀንቲናዎች በጨዋታው በድምሩ 464 ቅብብሎችን ብቻ ሲያደርጉ፣ ስፔን ግን 852 ቅብብሎችን አድርጋለች። ነገር ግን እንደ እንግሊዝ ሳይሆን፣ ስፔን በሁለተኛው አጋማሽ አልዛለችም፤ አልፈራችምም። ጨዋታው ቶሬስ በ106ኛው ደቂቃ ላይ ግብ ሳያስቆጥር ከብዙ ጊዜ በፊት በስፔን የበላይነት መጠናቀቅ ነበረበት። የአርጀንቲናው ግብ ጠባቂ ኤሚሊያኖ ማርቲኔዝ 11 ኳሶችን ለማዳን (Saves) የተገደደ ሲሆን፣ ይህም በዓለም ዋንጫ ፍፃሜ ታሪክ አንድ ግብ ጠባቂ ካደረጋቸው ማዳኖች ከፍተኛው ሆኖ ተመዝግቧል።
በተቃራኒው ደግሞ የወቅቱ ሻምፒዮናዎች የነበሩት አርጀንቲናዎች በዓለም ዋንጫ ታሪክ በመደበኛው የ90 ደቂቃ ጨዋታ ውስጥ ወደ ግብ አንድም ሙከራ ሳያደርጉ የወጡ የመጀመሪያው ቡድን በመሆን አሳፋሪ ታሪክ አስመዝግበዋል። የመጀመሪያው ሙከራቸው የመጣው በ117ኛው ደቂቃ ላይ በሊዮኔል ሜሲ አማካኝነት ነበር። አርጀንቲና የዓለም ዋንጫ አክሊሏን ብቻ ሳይሆን፣ ከጨዋታው መጠናቀቅ በኋላ ያሳየችው ባህሪ ክብሯንም ጭምር ያስገፈፋት ነበር።
ኤንዞ ፈርናንዴዝ በመጀመሪያ ለዳኛ ባለመታዘዝ ቢጫ ካርድ ከተመለከተ በኋላ፣ በፓው ኩባርሲ ላይ በሰራው እጅግ አደገኛና ዘግይቶ የመጣ ጥፋት (ታክል) በሁለተኛ ቢጫ ካርድ በካርድ ተባሯል። ጨዋታው ሲጠናቀቅ ደግሞ ሜዳው ወደ ቦክስ ስታዲየምነት ተቀይሮ ነበር! ፓሬዴስ ከሮድሪ፣ ጋቪ እና ቦርጃ ኢግሌሲያስ ጋር ወደ ግጭት ሲያመራ፣ ናሁኤል ሞሊና ደግሞ በዚያ ለሚያልፍ የስፔን ተጫዋች በቦክስ ሲሰነዝር ታይቷል።
ተንታኙ ዌይን ሩኒ ይህንን ክስተት ሲያወግዝ “ጨዋታው ከተጠናቀቀ በኋላ እንዲህ ዓይነቱን ነገር ማየት ፍጹም የሚያሳፍር ነው። አንድ ቡድን የዓለም ዋንጫ ሻምፒዮን ሆኖ ዘላለማዊ ክብሩን እያከበረ ባለበት ሰዓት እንዲህ ዓይነት ሁከት መፍጠር በጭራሽ ተቀባይነት የለውም። ፓሬዴስ ከዚህ የተሻለ ስብዕና ሊኖረው ይገባ ነበር፤ እሱ ግን ማቆም አልቻለም፤ አሁንም መጋፋቱን ቀጥሏል” ብሏል።
የአርጀንቲናው አሰልጣኝ ሊዮኔል ስካሎኒ ከጨዋታው በኋላ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ በዕንባ እየታጠቡ የቡድናቸውን እንቅስቃሴ ለመከላከል ቢሞክሩም፣ በመጨረሻ ግን ትክክለኛውና የተሻለው ቡድን ማሸነፉን አምነዋል። “ምንም እንኳን እስከ 85ኛው ደቂቃ ድረስ የበላይነታቸውን ቢያሳዩንም፣ ሜዳ ላይ 11 ተጫዋቾችን ይዘን ብንቆይ ኖሮ ምን ሊፈጠር እንደሚችል ማወቅ እፈልግ ነበር” ብለዋል ስለ ኤንዞ መባረር ሲናገሩ። አክለውም “ጨዋታው ክፍት በነበረበት ሰዓት እስከ መጨረሻው ለመጓዝ ሞክረን ነበር፣ ግን አልተሳካም። እነሱ ድሉ ይገባቸዋል፣ እውነታው ይህ ነው” ሲሉ ተናግረዋል።
አርጀንቲና ጨዋታውን ወደ ጭማሪ ሰዓት መውሰድ ብትችልም - ይህም ባለፉት ስድስት የዓለም ዋንጫዎች ውስጥ አምስቱ ጨዋታዎች ወደ ጭማሪ ሰዓት የሄዱበትን አጋጣሚ የደገመ ቢሆንም - ይህ ግን ሜዳ ላይ የነበራቸውን ፍጹም የበታችነት ሊሸፍንላቸው አልቻለም።
የቀድሞው የእንግሊዝ ግብ ጠባቂ ጆ ሃርት በበኩሉ “አርጀንቲናዎች ስለተፈጠረው ነገር ምንም ዓይነት ቅሬታ ሊኖራቸው አይገባም። ፍጹም አስጸያፊ ባህሪ ነው ያሳዩት። ሮድሪ ወደ እነሱ ፊት ሄዶ መጨቃጨቅ አልነበረበትም፤ ነገር ግን ለ120 ደቂቃዎች ሙሉ ስሜትህ ሲነካካና ዳኛው በአንተ ላይ ጫና ሲያደርግ ከቆየ በኋላ ድል ስታደርግ የሚሰማህን ስሜት መረዳት ይቻላል” ሲል ምሽቱን ቋጭቶታል።
በመጨረሻም ጥበብ አሸንፋለች፤ እግር ኳስም ነፃነቷን አውጃለች! ስፔን የዓለም አዲስ ንጉሥ ናት! 🇪🇸🏆
በጭማሪ ሰዓት ላይ ፌራን ቶሬስ ያንን ወርቃማ ግብ የአርጀንቲና መረብ ላይ ሲያሳርፈውና ሮድሪ ዋንጫውን ወደ ኒው ጀርሲ ሰማይ ከፍ አድርጎ ሲያነሳው፣ ለአርጀንቲና ብሔራዊ ቡድን ያዘነ ወይም ያነባ አንድም እውነተኛ የስፖርት አፍቃሪ አልነበረም። ስፔን የተጫዋቾችንም ሆነ የተመልካቾችን ትዕግሥት የፈተነውን ያንን አሰልቺ የአርጀንቲናውያንን የብረት መከላከያ ሰብራ በመውጣት፣ በታሪኳ ሁለተኛውን የዓለም ዋንጫ በደመቀ ሁኔታ አሳክታለች። በሁሉም የእግር ኳስ መለኪያዎች—አንዳንዶች እንደሚሉት ደግሞ በስፖርታዊ የሞራል ልዕልናም ጭምር - ይህ ፍፁም ትክክለኛና የሚገባ ውጤት ነበር።
የቀድሞው የእንግሊዝ ብሔራዊ ቡድን አጥቂ አላን ሽረር ላይ እንደተናገረው “ትክክለኛው ቡድን እንዳሸነፈ ምንም ጥርጥር የለውም። ከጅምሩ እስከ ፍፃሜው ስፔን የኳስ ቁጥጥር የበላይነቱን ወስዳለች። እግር ኳስ ለመጫወት፣ ዕድሎችን ለመፍጠርና ከተከላካይ ጀርባ ለመውጣት የሚጥሩት እነሱ ብቻ ነበሩ። ይህ ውጤት በተጫወቱበት ማራኪ መንገድ ምክንያት ለእግር ኳስ የተገኘ ትልቅ ድል ነው፤ ስፔን በእውነት ይገባታል።”
አኃዞቹ ራሳቸው እውነታውን በግልፅ ይመሰክራሉ። ስፔን 65% የኳስ ቁጥጥር፣ 1.94 የሚጠበቅ የግብ መጠን (xG) እና 20 ወደ ግብ የተደረጉ ሙከራዎችን (11ዱ ኢላማቸውን የጠበቁ) አስመዝግባለች። በአንፃሩ በሌላኛው የሜዳ ክፍል ግብ ጠባቂው ኡናይ ሲሞን በ8 ጨዋታዎች 7ኛውን ግቡን ሳያስደፍር በመውጣት የውድድሩ ምርጥ ግብ ጠባቂ በመሆን የጎልደን ግላቭ ሽልማትን አጋብሷል። ስፔን በጠቅላላው ውድድር ያስተናገደችው 1 ግብ ብቻ ሲሆን፣ ይህም በዓለም ዋንጫ ታሪክ አንድ ሻምፒዮን ቡድን ያስተናገደው አነስተኛው የግብ መጠን ሆኖ ተመዝግቧል።
የዓለም እግር ኳስን በአሁኑ ሰዓት በበላይነት እየመራ ያለው አንድ ኃይል ቢኖር እርሱም ስፔን ነው። በአሁኑ ወቅት የዓለም፣ የኦሊምፒክ እና የአውሮፓ ሻምፒዮን ናቸው - የሴቶች ቡድናቸው የዓለም ሻምፒዮን መሆኑ ሳይረሳ! የወንዶች ቡድናቸው በአሁኑ ወቅት ባደረጋቸው ያለፉት 38 ጨዋታዎች በሁሉም ውድድሮች ላይ ሽንፈት አላስተናገደም፤ ይህም በታሪክ የማንኛውም አውሮፓ ሀገር ረጅሙ ባለመሸነፍ ጉዞ ነው።
ምንም እንኳን በዚህ ውድድር መጀመሪያ ላይ ከኬፕ ቨርዴ ጋር 0ለ0 በሆነ አሰልቺ ውጤት በመጀመር አድናቂዎቻቸውን ቢያስደነግጡም፣ ልክ እንደ 2010ቱ የደቡብ አፍሪካ ዓለም ዋንጫ (በመጀመሪያው ጨዋታ በስዊዘርላንድ 1ለ0 ተሸንፈው እንደነበረው) የመክፈቻ ጨዋታቸውን ሳይያሸንፉ ቀርተው ዋንጫውን ማንሳት የቻሉበትን አስገራሚ አጋጣሚ በድጋሚ ደግመውታል።
በዓለም ዋንጫ የፍፃሜ ታሪክ ውስጥ አንድ ተጫዋች 100 እና ከዚያ በላይ ኳሶችን አቀብሎ ያጠናቀቀባቸው ሦስት አጋጣሚዎች ብቻ ሲሆኑ፣ ከእነዚህ ውስጥ ሁለቱ የተመዘገቡት በዚህ ምሽት በስፔን ተጫዋቾች ነው - ሮድሪ 101 ቅብብሎችን ሲያደርግ፣ የ19 ዓመቱ ታምረኛ ተከላካይ ፓው ኩባርሲ ደግሞ 121 ስኬታማ ቅብብሎችን አድርጓል።
ለዚህ ወጣት ቡድን ይህ ገና ጅምር ነው! ኩባርሲ የውድድሩ ምርጥ ወጣት ተጫዋች ሲባል፣ የባርሴሎና የቡድን አጋሩ ላሚን ያማል ደግሞ ገና ወደፊት ብዙ የሚያሳያቸው ወርቃማ ዓመታት ከፊቱ ይጠብቁታል። በ19 ዓመት ከ6 ቀን ዕድሜው ላሚን ያማል ከፔሌ (1958) እና ከጁሴፔ ቤርጎሚ (1982) በመቀጠል በዓለም ዋንጫ ፍፃሜ ላይ የተጫወተ ሦስተኛው ታናሽ ተጫዋች እና ሦስተኛው ታናሽ የዓለም ዋንጫ አሸናፊ መሆን ችሏል።
አርጀንቲናዎች በዓለም እግር ኳስ መድረክ ላይ ብዙ ጊዜ “ጨካኝና ተንኮለኛ” ተደርገው ይሳላሉ - በተለይም በእንግሊዝ ደጋፊዎች ዘንድ። በግማሽ ፍፃሜው ላይ በእንግሊዝ ላይ እንዳደረጉት ሁሉ፣ በዚህም ጨዋታ በመጀመሪያው አጋማሽ ላይ እግር ኳስ ለመጫወት ሳይሆን፣ የሜዳውን ውበትና የስፔንን እንቅስቃሴ ለማደናቀፍ ብቻ ትኩረት አድርገው ነበር የገቡት። ሊአንድሮ ፓሬዴስ ዋነኛው የጨዋታ አበላሺ ሲሆን፣ ኤንዞ ፈርናንዴዝ ደግሞ የእሱ ምክትል ረዳት ነበር። ምንም እንኳን አራት የአርጀንቲና ተጫዋቾች ቢጫ ካርድ ቢመለከቱም፣ ብዙዎች ግን ዳኞች ለአርጀንቲና አሁንም ቢሆን ርኅራኄ አሳይተዋል የሚል እምነት አላቸው።
አርጀንቲናዎች በጨዋታው በድምሩ 464 ቅብብሎችን ብቻ ሲያደርጉ፣ ስፔን ግን 852 ቅብብሎችን አድርጋለች። ነገር ግን እንደ እንግሊዝ ሳይሆን፣ ስፔን በሁለተኛው አጋማሽ አልዛለችም፤ አልፈራችምም። ጨዋታው ቶሬስ በ106ኛው ደቂቃ ላይ ግብ ሳያስቆጥር ከብዙ ጊዜ በፊት በስፔን የበላይነት መጠናቀቅ ነበረበት። የአርጀንቲናው ግብ ጠባቂ ኤሚሊያኖ ማርቲኔዝ 11 ኳሶችን ለማዳን (Saves) የተገደደ ሲሆን፣ ይህም በዓለም ዋንጫ ፍፃሜ ታሪክ አንድ ግብ ጠባቂ ካደረጋቸው ማዳኖች ከፍተኛው ሆኖ ተመዝግቧል።
በተቃራኒው ደግሞ የወቅቱ ሻምፒዮናዎች የነበሩት አርጀንቲናዎች በዓለም ዋንጫ ታሪክ በመደበኛው የ90 ደቂቃ ጨዋታ ውስጥ ወደ ግብ አንድም ሙከራ ሳያደርጉ የወጡ የመጀመሪያው ቡድን በመሆን አሳፋሪ ታሪክ አስመዝግበዋል። የመጀመሪያው ሙከራቸው የመጣው በ117ኛው ደቂቃ ላይ በሊዮኔል ሜሲ አማካኝነት ነበር። አርጀንቲና የዓለም ዋንጫ አክሊሏን ብቻ ሳይሆን፣ ከጨዋታው መጠናቀቅ በኋላ ያሳየችው ባህሪ ክብሯንም ጭምር ያስገፈፋት ነበር።
ኤንዞ ፈርናንዴዝ በመጀመሪያ ለዳኛ ባለመታዘዝ ቢጫ ካርድ ከተመለከተ በኋላ፣ በፓው ኩባርሲ ላይ በሰራው እጅግ አደገኛና ዘግይቶ የመጣ ጥፋት (ታክል) በሁለተኛ ቢጫ ካርድ በካርድ ተባሯል። ጨዋታው ሲጠናቀቅ ደግሞ ሜዳው ወደ ቦክስ ስታዲየምነት ተቀይሮ ነበር! ፓሬዴስ ከሮድሪ፣ ጋቪ እና ቦርጃ ኢግሌሲያስ ጋር ወደ ግጭት ሲያመራ፣ ናሁኤል ሞሊና ደግሞ በዚያ ለሚያልፍ የስፔን ተጫዋች በቦክስ ሲሰነዝር ታይቷል።
ተንታኙ ዌይን ሩኒ ይህንን ክስተት ሲያወግዝ “ጨዋታው ከተጠናቀቀ በኋላ እንዲህ ዓይነቱን ነገር ማየት ፍጹም የሚያሳፍር ነው። አንድ ቡድን የዓለም ዋንጫ ሻምፒዮን ሆኖ ዘላለማዊ ክብሩን እያከበረ ባለበት ሰዓት እንዲህ ዓይነት ሁከት መፍጠር በጭራሽ ተቀባይነት የለውም። ፓሬዴስ ከዚህ የተሻለ ስብዕና ሊኖረው ይገባ ነበር፤ እሱ ግን ማቆም አልቻለም፤ አሁንም መጋፋቱን ቀጥሏል” ብሏል።
የአርጀንቲናው አሰልጣኝ ሊዮኔል ስካሎኒ ከጨዋታው በኋላ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ በዕንባ እየታጠቡ የቡድናቸውን እንቅስቃሴ ለመከላከል ቢሞክሩም፣ በመጨረሻ ግን ትክክለኛውና የተሻለው ቡድን ማሸነፉን አምነዋል። “ምንም እንኳን እስከ 85ኛው ደቂቃ ድረስ የበላይነታቸውን ቢያሳዩንም፣ ሜዳ ላይ 11 ተጫዋቾችን ይዘን ብንቆይ ኖሮ ምን ሊፈጠር እንደሚችል ማወቅ እፈልግ ነበር” ብለዋል ስለ ኤንዞ መባረር ሲናገሩ። አክለውም “ጨዋታው ክፍት በነበረበት ሰዓት እስከ መጨረሻው ለመጓዝ ሞክረን ነበር፣ ግን አልተሳካም። እነሱ ድሉ ይገባቸዋል፣ እውነታው ይህ ነው” ሲሉ ተናግረዋል።
አርጀንቲና ጨዋታውን ወደ ጭማሪ ሰዓት መውሰድ ብትችልም - ይህም ባለፉት ስድስት የዓለም ዋንጫዎች ውስጥ አምስቱ ጨዋታዎች ወደ ጭማሪ ሰዓት የሄዱበትን አጋጣሚ የደገመ ቢሆንም - ይህ ግን ሜዳ ላይ የነበራቸውን ፍጹም የበታችነት ሊሸፍንላቸው አልቻለም።
የቀድሞው የእንግሊዝ ግብ ጠባቂ ጆ ሃርት በበኩሉ “አርጀንቲናዎች ስለተፈጠረው ነገር ምንም ዓይነት ቅሬታ ሊኖራቸው አይገባም። ፍጹም አስጸያፊ ባህሪ ነው ያሳዩት። ሮድሪ ወደ እነሱ ፊት ሄዶ መጨቃጨቅ አልነበረበትም፤ ነገር ግን ለ120 ደቂቃዎች ሙሉ ስሜትህ ሲነካካና ዳኛው በአንተ ላይ ጫና ሲያደርግ ከቆየ በኋላ ድል ስታደርግ የሚሰማህን ስሜት መረዳት ይቻላል” ሲል ምሽቱን ቋጭቶታል።
በመጨረሻም ጥበብ አሸንፋለች፤ እግር ኳስም ነፃነቷን አውጃለች! ስፔን የዓለም አዲስ ንጉሥ ናት! 🇪🇸🏆
19 days ago
⚠️ ለአሽከርካሪዎች የተላለፈ መልዕክት፡ የቢጫ ሳጥን ምልክት (Yellow Box Junction) ምንድነው? እንዴትስ እንጠቀምበት?
በቅርቡ በከተማችን መንገዶች ላይ ተግባራዊ መሆን ስለጀመረው የቢጫ ሳጥን ምልክት (Yellow Box Junction) ምን ያህል ያውቃሉ?
ይህ ምልክት በመጋጠሚያዎች ላይ የሚሳል፣ የተያያዙ መስመሮች ያሉት ቢጫ ሳጥን ሲሆን፣ ዋና ዓላማው የመንገድ መጋጠሚያዎች ሁልጊዜም ክፍት እንዲሆኑ ማድረግ እና የትራፊክ መጨናነቅን መከላከል ነው።
🎯 የቢጫ ሳጥን ምልክት ጥቅሞች፡
📍መንገድ እንዳይዘጋ ይረዳል፦ መጋጠሚያዎች በማናቸውም ሰዓት ክፍት ሆነው እንዲቆዩ ያደርጋል።
📍የትራፊክ ፍሰትን ያሻሽላል፦ አቋራጭ መንገድ ለሚጠቀሙና ለድንገተኛ አደጋ ተሽከርካሪዎች (አምቡላንስና እሳት አደጋ) ፈጣን መተላለፊያ ይሰጣል።
📍አደጋን ይከላከላል፦ በመጋጠሚያዎች ላይ የሚከሰቱ የተሽከርካሪዎች መጋጨት አደጋዎችን በከፍተኛ ሁኔታ ይቀንሳል።
🛑 ዋናውና ወሳኙ ህግ (አሽከርካሪዎች ሊያውቁት የሚገባ!)፦
"ከፊትዎ ያለው መንገድ ሙሉ በሙሉ ክፍት ካልሆነና ሳጥኑን ሳያቋርጡ መቆም የሚኖርብዎት ከሆነ፣ በፍጹም ወደ ቢጫው ሳጥን ውስጥ አይግቡ!"
መቼ መግባት ይቻላል? ከሳጥኑ ማዶ ያለው መንገድ ክፍት መሆኑንና ሳይቆሙ በቀጥታ ማለፍ የሚችሉ መሆንዎን እርግጠኛ ሲሆኑ ብቻ።
መቼ መግባት የተከለከለ ነው? ከሳጥኑ ባሻገር ያለው መንገድ በትራፊክ መጨናነቅ ምክንያት ዝግ ከሆነ፣ አረንጓዴ መብራት ቢበራልዎት እንኳ ሳጥኑ ውስጥ ገብቶ መቆም በጥብቅ የተከለከለ ነው!
💡 ውድ አሽከርካሪዎች፦ ይህንን የትራፊክ ምልክት በወጉ በመገንዘብ፣ ደንቡን አክብረን በማሽከርከር እና መረጃውን ለሌሎች በማጋራት የበኩላችንን እንወጣ። ራሳችንንም ካላስፈላጊ የደንብ መተላለፍ ቅጣት እንጠብቅ!
በቅርቡ በከተማችን መንገዶች ላይ ተግባራዊ መሆን ስለጀመረው የቢጫ ሳጥን ምልክት (Yellow Box Junction) ምን ያህል ያውቃሉ?
ይህ ምልክት በመጋጠሚያዎች ላይ የሚሳል፣ የተያያዙ መስመሮች ያሉት ቢጫ ሳጥን ሲሆን፣ ዋና ዓላማው የመንገድ መጋጠሚያዎች ሁልጊዜም ክፍት እንዲሆኑ ማድረግ እና የትራፊክ መጨናነቅን መከላከል ነው።
🎯 የቢጫ ሳጥን ምልክት ጥቅሞች፡
📍መንገድ እንዳይዘጋ ይረዳል፦ መጋጠሚያዎች በማናቸውም ሰዓት ክፍት ሆነው እንዲቆዩ ያደርጋል።
📍የትራፊክ ፍሰትን ያሻሽላል፦ አቋራጭ መንገድ ለሚጠቀሙና ለድንገተኛ አደጋ ተሽከርካሪዎች (አምቡላንስና እሳት አደጋ) ፈጣን መተላለፊያ ይሰጣል።
📍አደጋን ይከላከላል፦ በመጋጠሚያዎች ላይ የሚከሰቱ የተሽከርካሪዎች መጋጨት አደጋዎችን በከፍተኛ ሁኔታ ይቀንሳል።
🛑 ዋናውና ወሳኙ ህግ (አሽከርካሪዎች ሊያውቁት የሚገባ!)፦
"ከፊትዎ ያለው መንገድ ሙሉ በሙሉ ክፍት ካልሆነና ሳጥኑን ሳያቋርጡ መቆም የሚኖርብዎት ከሆነ፣ በፍጹም ወደ ቢጫው ሳጥን ውስጥ አይግቡ!"
መቼ መግባት ይቻላል? ከሳጥኑ ማዶ ያለው መንገድ ክፍት መሆኑንና ሳይቆሙ በቀጥታ ማለፍ የሚችሉ መሆንዎን እርግጠኛ ሲሆኑ ብቻ።
መቼ መግባት የተከለከለ ነው? ከሳጥኑ ባሻገር ያለው መንገድ በትራፊክ መጨናነቅ ምክንያት ዝግ ከሆነ፣ አረንጓዴ መብራት ቢበራልዎት እንኳ ሳጥኑ ውስጥ ገብቶ መቆም በጥብቅ የተከለከለ ነው!
💡 ውድ አሽከርካሪዎች፦ ይህንን የትራፊክ ምልክት በወጉ በመገንዘብ፣ ደንቡን አክብረን በማሽከርከር እና መረጃውን ለሌሎች በማጋራት የበኩላችንን እንወጣ። ራሳችንንም ካላስፈላጊ የደንብ መተላለፍ ቅጣት እንጠብቅ!
Sponsored by
Surafel
20 days ago
የአገሪቱን የመስኖ ሽፋን ወደ 2.6 ሚሊዮን ሄክታር ለማድረስ የተያዘው ግብ እመርታ እያሳየ መሆኑ ተገለጸ
የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስቴር
መግለጫ እነሆ ፥
#ethiopia | አገራዊ የመስኖ ልማት ጉዞ ተስፋ ሰጪ እመርታ የኢትዮጵያ በመስኖ የመልማት አቅሟን፤ ለመጠቀምና ተፈጥሮ የለገሰቻትን ውሃ፣ መሬት፣ ምቹ የአየር ሁኔታ እንደዚሁም አምራች የሰውሃይል በአግባቡ መጠቀም ባለመቻሏ ለዘመናት የራሷን የምግብ አቅርቦት እንኳን መሸፈን ሳትችልና በችግር ወቅት ለዕርዳታ ወደ ውጪ ስታማትር መኖሯ የቅርብ ጊዜ ታሪካችን ነው፡፡
ኢትዮጵያን በተለያየ ጊዜያት ያስተዳደሩ መንግስታት ምርታማነት ለማሳደግ ያስችለናል ያሏቸውን የተለያዩ ሙከራዎች በመከተል ጥረት ቢያደርጉም በሚጠበቀው ልክ ውጤታማ ሳይሆኑ ቀርተዋል፡፡ በዚህም ሳቢያ አገራችን የራሷን የምግብ አቅርቦት መሸፈን ሳትችል፣ በቢሊዮን የሚቆጠር የውጭ ምንዛሬ በማውጣት ስንዴን ጨምሮ የተለያዩ የምግብ ምርቶችን ከውጭ ስታስገባ ኖራለች።
እንደ ሃገር ሰፋፊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ከ1960ዎቹ ጀምሮ መተግበር ቢጀምሩም ቁጥራቸው እጅግ ጥቂትና ውጤታቸውም በዛው ልክ ውስን እንደነበር በመስኩ የተደረጉ የዳሰሳዎች ጥናቶች ያሳያሉ ፡፡ ለአብነትም ለስኳር ልማት የተገነቡ ፕሮጀክቶች እንደ ወንጂ፣ መተሃራ፣ ፊንጫ ፣ የአሚባራ፣ የአልዌሮ፣ የጎዴ፣ የተንዳሆ እና የከሰም መስኖ ልማት ፕሮጀክቶች ተጠቃሾች ቢሆኑም በትግበራ ሂደት ግን ለአመታት ባጋጠሙ ተግዳሮቶች ውጤታማ ሳይሆኑ መቆየታቸው ይታወቃል፡፡
ይህንን አዙሪት በመስበርና የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ፣ ከተፈጥሮ ዝናብ ባሻገር የከርሰ-ምድርና የገጸ-ምድር ውኃን በአግባቡ በመጠቀም መስኖን ማስፋፋት ወሳኝ ሆኖ ተገኝቷል። በተለይም ባለፉት የለውጥ አመታት የኢትዮጵያ መንግስት ከዚህ የተለመደና ፈተና የሆነ አዙሪት ለመላቀቅ የሚያስችሉ የተለያዩ እቅዶችን አዘጋጅቶ እና ዘርፉን ራሱን በቻለ ሚኒስቴር መስራቤት ደረጃ በማደራጀት አዲስ የፖሊሲ መር የልማት ጥረትን ተግባራዊ ለማድረግ የሚያስችል ስራ መስራት ጀምሯል፡፡
መንግስት የኢትዮጵያን የምግብ ሉአላዊነት ለማረጋገጥ ከወሰዳቸው ወሳኝ እርምጃዎች መካከል የመስኖ ልማት ዘርፍን ውጤታማ በሆነ መንገድ በማሻሻል ምርታማነትን ማሳደግ እንዲቻል ዘርፋ ለአጠቃላይ አገራዊ እድገት የሚኖረውን ሚናም በልዩ ትኩረት ለማሳደግ እንዲያስችለው መስኖ በጥናት በተለዩ ቦታዎች ላይ በልዩ ትኩረት እንዲያስፋፋ በማለም የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስቴርን በ2014 ዓ/ም እንዲቋቋም አድርጓል፡፡ በዚህም የአገር አቅም በፈቀደ ልክም መንግስት ለዘርፉ ከፍተኛ በጀት እንዲመደብለት እና በዘርፉ ተግባራዊ ለውጥ እንዲመጣ የሚያስችሉ ስራዎችን ሲሰራ ቆይቷል ፡፡
የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስቴርም የመስኖና ቆላማ አካባቢ ልማትን ወደ ተቀናጀ የልማት አቅጣጫ በመምራት፤ ሀገራችን ያላትን ከፍተኛ የውሃና ሰፊ የመሬት ሀብት ማዕከል በማድረግ፤ የመስኖ ልማትን በማስፋፋት እና በቆላማ አካባቢ የሚገኘውን እምቅ የልማት ፀጋዎችን በማጥናትና ለአርብቶአደሩና ከፊልአርብቶአደሩ ጥቅም እንዲዉል በማድርግ የሀገራችንን የምግብ ሉዓላዊነት እንዲረጋገጥ ለማስቻል መተግበር የጀመራቸውም ስራዎች አመርቂ ውጤቶች ማሳየት ጀምረዋል፡፡
መስሪያ ቤቱ ግዙፍ የመስኖ ፕሮጀክቶችን በማስጠናትና በመገንባት፤በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ እና በክልሎች የሚገቡ አነስተኛ መስኖዎችን በመከታተልና ድጋፍ በመስጠት በሃገሪቱ ምርትና ምርታማነት ላይ ተጨባጭ ለውጥ ማምጣት ያስቻሉ ተግባራትን መጀመሩም ከወዲሁ መታዘብ ይቻላል፡፡
በተለይ ደግሞ ባለፋት ሁለት የበጀት አመታት ማለትም በ2017 እና 2018 በጀት ዓመት በኢትዮጵያ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ አፈጻጸም ዙርያ የተከናወኑ ስራዎች በአጠቃላይ በዘርፋ የሚታዩ ጅምር ሙከራዎችን ወደ አዲስ ታሪክ ያሸጋገረ ምዕራፍ ላይ መድረሱን መታዘብ ይቻላል።
ዘርፋ ከተሰጠው ልዩ ትኩረትና በአገር አቀፍ ደረጃ የመስኖ ልማት ጥያቄዎች መበራከት ከጅምሩ በቂ ጥናቶችና የዲዛይን ስራዎች ጥልቅ የበጀት ዝግጅትና በከፍተኛ የህዝብና የመንግስት አመራር ማእቀፎች በቂ ውይይት ተደርጎባቸው እንዲሁም የአፈጻጸም ስጋቶችና በተለይም ከአጠቃላይ የበጀት ዝግጅቶች አንጻር በነበሩ ውስንነቶች ጉልህ ችግሮች የነበሩ ቢሆንም ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ከህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እና ከገንዘብ ሚኒስቴር ጋር በፍጥነት በመመካከር መሰረታዊ የማጣጣም ስራዎች መከወን በመቻሉ በርካታ ስራዎችን በተከታታይ ወራት በስኬት ሐዲድ ለማስጓዝ ተችሏል።
በዚህም በነዚህ ሁለት አመታት ለበርካታ አመታት ግንባታቸው የተጓተቱ ፣ የዲዛይን ስራ ጉድለቶች የነበሩባቸው ተጠናቀውም ለረጅም ጊዜ ጥገና ያልተደረገላቸው እና ከፍተኛ ብልሽት አጋጥሟቸው የነበሩ ፕሮጀክቶችን ቁርጠኛ በሆነ የፕሮጀክት አመራር ክትትል እና ጥብቅ የኮንትራት አስተዳደር ስርዓትን መሰረት በማድረግ ፕሮጀክቶችን በማጠናቀቅ አመርቂ ውጤቶች ተመዝግበዋል፡፡
ለዚህ ስኬት ሚኒስቴር መስሪያ ቤታችንም መንግስት የኢትዮጵያን የምግብ ሉአላዊነት ለማረጋገጥ ያለውን ፅኑ ፍላጎትና እያደረገ ያለውን ከፍተኛ ድጋፍ ከግንዛቤ በማስገባት ይህንንም በሚመጥን መልኩ ተገቢውን ትኩረት ሰጥቶ በጥራት በፍጥነት እና የኮንትራት ስምምነቶችን መሰረት በማድረግ የሰጠው በሳል አመራርም ተጠቃሽ ምክንያት ነው።
በዚህም ምክንያት ለአመታት የዘገዩና የማህበረሰባችን የአመታት የቅሬታ ምንጨ ሆነው የኖሩትን በአጠቃላይ 10 የሚሆኑ ግዙፍ የመስኖ ፕሮጀክቶችን በአጭር ግዜ ከውስብስብ ችግሮች በማላቀቅ በልዩ ትኩረት ቅድሚያ በተሰጣቸው አቅጣጫ መሰረት በተፋጠነ ጊዜ እንዲጠናቀቁ ጥረት ተደርጓል።
እነዚህም የመስኖ መሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች የማልማት አቅማቸው እና ተጠቃሚ የሚያደርጉት እማና አባ ወራወዎች በቅደም ተከተላቸው መሰረት የሚከተሉት ናቸው ፡-
1.ጊዳቦ ሎት 2 - የማልማት አቅሙ- 13420 ሄ/ር 26840 እማ/አባወራዎች
2. ጎዴ -የማልማት አቅሙ -10,000 ሄ/ር 20000 እማ/አባወራዎች
3. ወልመል ሎት 1 እና 2 – 12040 ሄ/ር -24080 እማ/አባወራዎች
4. ጨልጨል ሎት 2- 4145 ሄ/ር 8290 እማ/አባወራዎች
5.የቄጦ መስኖ 5000 ሄ/ር 10,000 እማ/አባወራዎች
6. የታችኛው ርብ -3200 ሄ/ር 6400 እማ/አባወራዎች
7. የተንዳሆ - 60,000 ሄ/ርያለማል 120,000 እማ/አባወራዎች
8. የከሰም መስኖ -20 ሺኅ ሄ/ር 40,000 እማ/አባወራዎች
እንዲሁም አርጆ ዲዴሳ እና መገጭ መስኖ ልማት ፕሮጀክቶች መሠረታዊ የግንባታ ሥራቸው አልቆ የማጠናቀቂያ ሥራቸው እየተፋጠነ ከመሆኑም በላይ በቅርቡ በክብር የሚመረቁ ይሆናል፡፡
መገጭ እና አርጆ የመስኖ ፕሮጀክቶች ሲጠናቀቁ በአጠቃላይ የ10ሩ ፕሮጀክቶች ብቻ ድምር የማልማት አቅማቸው 224,805 ሄክታር ሲሆን 450,000 እማና አባወራዎችን ተጠቃሚ የሚደርጉ ናቸው፡፡
በሌላ በኩል እንደ ጨልጨል (ሎት1) አጂማጫጫ፣ ካሊድ ዲጆ፣ ሎጊያ፣ ላይኛው ጉደር፣ አንገር ፣ ፈንታሌ፣ ወይቦ፣ ላይኛው ርብ፣ ሽንሌ፣ እና አደኣ በቾ የመስኖ መሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች በዕቅዳቸው መሠረት የግንባታ ስራዎቻቸው እየተከናወ ባጠናቀቅናቸው የመስኖ ፕሮጀክቶች በአሁኑ ወቅት ሰፋፊ የእርሻ መሬቶችን በማልማት የማህበረሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተቀናጁ ስራዎች በመተግበር ላይ እንገኛለን፡፡
መንግስት ለመስኖ ልማቱ ዘርፍ በሰጠው ከፍተኛ ትኩረት በተሰሩ ስራዎች ከለውጡ በፊት 490 ሺህ ሄክታር የነበረው የመስኖ ሽፋን ወደ 2.6 ሚሊዮን ሄክታር ከፍ እንዲል አድርጓል፡፡ አሁን የተጀመሩ ፕሮጀክቶችም ሲጠናቀቁ የአገራችን የመስኖ ሽፋን በከፍተኛ መጠን የሚጨምር ይሆናል፡፡ እነዚህ መሰረተ ልማቶችም የተጀመረውን የኢትዮጵያን የምግብ ሉአላዊነት በማረጋገጥ ረገድ የሚኖራቸው ሚና ከፍተኛ ነው፡፡
በ2017 እና በ2018 በጀት አመት ፕሮጀክቶች አጠናቅቀን ለስኬት ስንበቃ ፤ ግንባታዎች ባቀድነው ጊዜ እንዳይጠናቀቁ ስያደርጉ የቆዩትን፣ እንደዚሁም በቀጣይነትም ስራን ሊያስጓጉሉ የሚችሉትን ቁልፍ ማነቆዎች በጥናት በመለየት ውስብስብ ለሆኑና ለቆዩ ችግሮች ተገቢ እና ህጋዊ መፍትሄ እንዲያገኙ በማድረግ ረገድ የተሰሩ ስራዎች ሚናቸው ትልቅ ነው፡፡
በመሆኑም ይህ ፈጣን የፕሮጀክት አፈጻጸም እና ክትትል በቀላሉ የተገኘ እንዳልሆነ መገንዘብ ያሻል።
ለመሆኑ በእነዚህ የግንባታ 2 አመታት እንደማንኛውም የኮንስትራክሽን ዘርፍ የመስኖ ግንባታ ያጋጠሙት ተግዳሮቶች ምንድናቸው? የተሰጣቸው መፍትሔዎችስ ?
በግንባታ ሂደቱ ያጋጠሙንን ተጠባቂና ተጠባቂ ያልሁኑ ተግዳሮቶች ተወጥተን የግንባታ ስራችንን ስናከናውን በግንባታ ሂደቱ ላይ ተፅዕኖ ያሳደሩ ዋና ዋና ተግዳሮቶችን የሚከተሉት ናቸው፦
* የመስኖ ልማት ፕሮጀክቶች ከውኃ ጋር የተቆራኙና በካበተ የዘርፍ ጥናት የተደገፋ መሆን የሚገባቸው በመሆናቸው በዘርፉ ልምድ ያላቸው በቂ አገር በቀል የአማካሪና ተቋራጮች አቅም በበቂ አለመኖሩ ከጅምሩ የታዩ ተግዳሮቶች ነበሩ:: በተጨማሪም አብዛኞቹ ፕሮጀክቶች የሚከናወኑት በመንግስት የልማት ድርጅቶች ሲሆን ተቋማቱ በዘርፋ ለሚደረግ የመሰረተ ልማት ግንባታ የነበራቸው ልምድና አቅምም ውስን ከመሆኑም በላይ ከግሉ ዘርፍ የሚሳተፉት በጣት የሚቆጠሩ ተቋማትም ገና አጥጋቢ ቁመና ያልነበራቸው መሆኑ።
* የበጀት እጥረትና የገንዘብ አቅርቦት መዘግየት፦ ፕሮጀክቶቹ ከፍተኛ ሀብት የሚጠይቁ ቢሆንም በየዓመቱ የሚመደበው በጀት አነስተኛ መሆኑና የተፈቀደው በጀትም በወቅቱ ጥሬ ገንዘብ ሆኖ ባለመለቀቁ ከክፍያዎች መስተጓጎል የተነሱ መጓተቶችና የዋጋ ንረት ፕሮጀክቶች በሚፈለገው ደረጃ ማከናወን አለመቻሉ፣
* ከፍተኛ የገበያ የዋጋ ንረት (Market Inflation)፦ ከ2013 ዓ.ም ጀምሮ በዓለም አቀፍና አገር ውስጥ ሁኔታዎች ምክንያት እንደ ሲሚንቶ፣ ብረት፣ ነዳጅ እና የጉልበት ዋጋ ላይ በየግዜው ከፍተኛ ጭማሪ ማጋጠሙ። በዚህም ምክንያት የፕሮጀክት በዘገዩ ቁጥር ወጪዎቻቸው በየግዜው እንዲጨምሩ ምክንያት ሆነዋል ::
* የስትራቴጂካዊ ግንባታ ዕቃዎች አቅርቦት እጥረት፦ ሲሚንቶ፣ ብረትና ነዳጅ በገበያ ላይ በበቂ ሁኔታ በወቅቱ አለመገኘታቸው የግንባታውን ፍጥነት በእጅጉ ገድበውት ቆይተዋል። በዚህም ምክንያት ፕሮጀክቶች በእቅዳቸው ልክ እንዳይከወኑ ምክንያት ሆኖ ቆይቷል ::
* የግድብ እና መስኖ መሰረተ ልማቶች ዲዛይን ስራዎች ጉልህ ክፍተቶችና ያጋጠሙ የጂኦሎጂካል ውስብስብነት ችግሮች :: ምንም እንኳን ፕሮጀክቶች መነሻ የሚሆኑ ጥናትና ዲዛይን ተሠርቶባቸው ቢጀመሩም፣ በትግበራ ወቅት በሚያጋጥሙ የመሬት አቀማመጥና የጂኦሎጂካል ይዘቶች ምክንያት የዲዛይን ክለሳዎችን ማድረግ የግድ ማስፈለጉ የውል ማሻሻያዎችንና የጊዜ ማራዘሚያዎችን እንዲደረጉ የግድ የሚያስብሉ ሁኔታዎች አጋጥመዋል ::
በዚህም ምክንያት ለሚኖሩ ለውጦች ተጨማሪ የኮንትራት ወጪ እና ግዜ መጠየቃቸው የግድ ሆኗል።
የተወሰዱ ስልታዊና መዋቅራዊ የማስተካከያ እርምጃዎች የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስቴር ከዚህ በፊት በተደጋጋሚ ያጋጠሙትን የአሠራር ክፍተቶች፣ የኦዲት ግኝቶችና የባለድርሻ አካላትን አስተያየቶች እንደ ግብዓት በመውሰድ ሰፊ ተቋማዊ ለውጥ (Institutional Reform) አድርጓል።
በዚህም መሠረት የተወሰዱት ቁልፍ ተቋማዊ እርምጃዎች የሚከተሉት ናቸው፦
* ልዩ የፕሮግራም ማስተባበሪያ ጽሕፈት ቤት በአዲስ መልክ በ2017ዓ/ም ተቋቁሟል ፦ከዋናው መሥሪያ ቤት እስከ ፕሮጀክት ሳይት የነበረውን የቁጥጥር እና ክትትል ለማጥበቅና የውል አስተዳደር እንዲሁም የቁጥጥር ሥርዓቱን (Contract Administration & Construction supervision) በዲጂታል ፕላትፎርም ጭምር ለማዘመን ዘርፈ-ብዙ ብቁ ባለሙያዎችን ያቀፈ ፕሮጀክት ጽሕፈት ቤት ተቋቁሟል።
* ጥብቅ የክትትልና ግምገማ (M&E) ሥርዓት መዘርጋት፦የዲጂታል ቴክኖሎጂን በመጠቀም ዕለታዊ፣ ሳምንታዊ፣ወርሃዊ፣ ሩብ ዓመት፣ ግማሽ ዓመት እና ዓመታዊ የክትትልና የመስ ክምልከታ ሥርዓት ተዘርግቶ ተግባራዊ ሆኗል።
* በኮንትራት ስምምነት መሰረት ለፕሮጀክቶች ክትትል የሚያስፈልገውን ሎጅስቲክስ እንዲሟላ ተደርጓል፥- በአዲስ መልክ ለተደራጀዉ ፕሮግራም ጽ/ቤት ከማዕከል እስከ ፕሮጀክት ሳይት ለተመደቡ የስራ መሪዎችና ሙያተኞች የሚያስፈልጉ የመስክን ነባራዊ ሁኔታ የሚቋቋሙ የመስክ ተሽከርካሪዎች እና የቢሮ ቁሳቁሶችን በኮንትራት ስምምነት ውስጥ በተቀመጠው መሰረት በማሟላት የክትትል አመራሮች እና ባለሙያዎች በተቀናጀ መልኩ ጉልበታችዉና እውቀታቸዉን ለፕሮጀክቶቹ ስኬት የሚያውሉበትን ሁኔታ በመፍጠር በጊዜና በጥራት ፕሮጀክቶችን በማጠናቀቅ ውጤታማ ስራ እየተመዘገበ ይገኛል::
* የቁሳቁስ አቅርቦት ሰንሰለትን ማሳለጥ (Supply Chain Optimization)፦ የሲሚንቶ እና የነዳጅ እጥረትን ለመቅረፍ ሚኒስቴሩ በቀጥታ ከአምራች ፋብሪካዎችና አቅራቢዎች ጋር ስልታዊ ትስስር በመፍጠር የግንባታ ግብዓቶች ሳይቆራረጡ ፕሮጀክት ሳይት ላይ እንዲቀርቡ አድርጓል።
* ባለሦስት ወገን ስምምነት (Tri-party Agreement) መተግበር፦ በተቋራጭ፣ በአማካሪ መሐንዲስ፣ በባለቤት(ሚኒስቴሩ) እና በቁሳቁስ አቅራቢዎች መካከል የተቀናጀ የጋራ መግባቢያ ስምምነት በመፈረም ሥራዎች በተቀመጠላቸው ወሰን፣ በጀትና ጥራት ኮንትራት መሰረት አድርገው እንዲከናወኑ ተደርጓል።
* አዳዲስ መመሪያዎችና ስታንዳርዶች ማዘጋጀት፦ ወደፊት ለሚከናወኑ ማናቸውም ግንባታዎች መነሻ የሚሆኑ የፕሮጀክት አስተዳደርን የሚያዘምኑ አዳዲስ የአሠራር ደንቦችና መመሪያዎች ተዘጋጅተዋል።
* የዋጋ ማስተካከያ መፍቀድ፦ አገር በቀል ተቋራጮች ፕሮጀክቶች በወቅቱ መጠናቀቅ ባለመቻላቸው ያጋጠመውን የዋጋ ንረት በራሳቸ መቋቋም ባለመቻላቸው፣ በመንግስት የተቀመጡ አሠራሮችን በመከተል ቀደም ሲል የዋጋ ማስተካከያን ይከለክሉ የነበሩ ውሎችን ከ2013 ጀምሮ በተሰጠው የመንግስት ውሳኔ መሰረት ውሎችን በማሻሻል የዋጋ ማስተካከያ በሃገር ደረጃ እንዲደረግ ፈቅዷል።
* የበጀት እጥረትና የገንዘብ አቅርቦት መዘግየትን በተመለከተ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ከገንዘብ ሚኒስቴር ጋር በቅርበት በመወያየት እና በመስራት አስፈላጊው በጀት እና ጥሬ ገንዘብ በወቅቱ ለመስኖ ፕሮጀክቶች ቅድሚያ ተሰጥቶ እንዲለቀቁ ማድረግ ተችሏል፡፡
የመስኖ ፕሮጀክቶች እንደ ማንኛውም የግንባታ ፕሮጀክቶች መንግስት ባወጣው የግዥ መመሪያዎች፣ ደንቦች እና ውሎች የሚተዳደሩ ናቸው :: የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስቴር መ/ቤት ከሌሎች ተቋማት የተረከባቸውንም ሆነ በራሱ የጀመራቸውን ፕሮጀክቶች የሚያስተዳድረው የመንግስትን ህግና ስርአትን በማክበር በኮንትራት ውል ስምምነት መሰረት ብቻ ነው፡፡
በዚህም መሰረት በየግዜው ልዩ ፍቃድ የሚያስፈልጋቸው ጉዳዮች ሲያጋጥሙም በህግ የመፍቀድ መብት ያለውን የመንግስት አካል ፍቃድ በማግኘት ብቻ የተፈፀሙ ስራዎችን መከወን ተችሏል ፡፡
ከመስኖ ፕሮጀክቶች ውስብስብ ባህሪ በመነሳት በተቻለ መጠን ባሉ ሀገራዊ አቅሞች እና ልምድና አቅም ባላቸው አማካሪ ድርጅቶች ዝርዝር ጥናትና ዲዛይን ሳይሰራ የመስኖ ፕሮጀክቶች አይጀመሩም፡፡ ሆኖም በትግበራ ወቅት የዲዛይን ክፍተቶች መኖራቸው ሲታወቅ በተቀመጠው የውል አስተዳደር ስምምነት መሰረት የፕሮጀክቶች የዲዛይን ችግር እንዲፈታ በማድረግ የተጀመሩ ፕሮጀክቶች በዲዛይን
ማሻሻያው መሰረት እንዲቀጥሉ እና እንዲጠናቀቁ ይደረጋሉ፡፡
ምንም እንኳን የዲዛይን ክፍተቶች ችግር ደረጃ ቢለያይም ፕሮጀክቶች በተግባር የዲዛይን ክፍተቶች እንደሚያጋጥማቸው ይታወቃል፡፡ ከፕሮጀክቶች ውል አስተዳደር አንፃርም ተቋራጭ እና አማካሪ ድርጅቶች በገቡት ውል መሰረት ብቻ ሚኒስቴር መ/ቤቱ ውሎችን ያስተዳድራል በዚህም የፕሮጀክቶች አፈጻጸም ውጤትም ይህንኑ ሀቅ ያረጋግጣል። በመሆኑም በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ከውል ውጪ የሚፈፀሙ ምንንም አይነት ግዥዎችና ጭማሪዎችም የሉም።
አለማቀፍ ልምዶች እንደሚያሳዩት ማንኛውም ፕሮጀክት ተግባራዊ በሚደረግባት ወቅት በገቢያ ሁኔታ ለሚከሰቱ የዋጋ ጭማሪዎች ተገቢውን አሰራር እና ኮንትራት ስምምነትን በመከተል የሚፈቀዱ የዋጋ ማስተካከያዎችን በማድረግ ፕሮጀክቶች ተግባራዊ ይደረጋሉ፡፡
በአገራችን ከ2013 ዓ.ም. ጀምሮ በከፍተኛ ሁኔታ የግንባታ ግብአቶች በመጨመሩ፣የነዳጅ ዋጋ በከፍተኛ ሁኔታ በመጨመሩ እና በአለማቀፍ ሁኔታዎች መለዋወጥ ምክንያት የግንባታ ሴክተሩ በከፍተኛ ሁኔታ ችግር ውስጥ ገብቶ ቆይተው የነበሩ ፕሮጀክቶች በመኖራቸውም እስካሁንም ከተመሳሳይ ችግሮች ሙሉ በሙሉ ለማገገም የሚያስችል ስራ መስራትም ቀጣይ የቤት ስራችን ይሆናል፡፡
በዚህም ምክንያት አገር በቀል ተቋራጭ ድርጅቶች የተከሰተውን የግንባታ ግብአቶች ከፍተኛ የዋጋ ጭማሪ በራሳቸው መቋቋም እንዳቃታቸው መንግስት በመገንዘቡ የተቀመጡ አሰራሮችን በመከተል የዋጋ ማስተካከያ እንዲደረግ ፍቃድ ሰጥቷል፡፡ በዚህም መሰረት ቀደም ሲል የዋጋ ማስተካከያ ይከለክሉ የነበሩ ውሎችን በማሻሻል የዋጋ መስተካከያ መፍቀድ እና ተግባራዊ ማድረግ ከፕሮጀክቱ መጠናቀቅ የሚያስገኘውን ጥቅም ቅድሚያ በመስጠት በተሰጠው ፍቃድ መሰረት ተግባራዊ ተደርጓል፡፡
ኢትዮጵያ በዝናብ ጥገኝነት ላይ የተመሠረተውን የግብርና ክፍለ-ኢኮኖሚ ወደ መስኖ መርና አስተማማኝ ምርታማነት ለመቀየር የጀመረችውን ጉዞ ስኬታማ ሊሆን የሚችለው አሁን የተጀመሩት ተቋማዊ ሪፎርሞች እና ፕሮጀክቶችን በማጠናቀቅ ወደ ውጤት የመቀየር ጅምሮች ቀጣይነት ሲኖራቸው ብቻ ነው። ይህንን ለማደናቀፍና ኮንትራትና ፕሮጀክት አስተዳደር ስርዓትን በአግባቡ መረዳት ባቃታቸው ወይም ሆን ተብሎ ሂደቶችን ለማጠልሸት የሚሰሩ ስራዎች በፍፁም ተቀባይነት ሊኖራቸው አይችሉም ::
እንደሚታወቀው ሃገራችን በተለያዩ ሴክተሮች አስደናቂ የሆኑ ስኬቶችን እያስመዘገበች ትገኛለች፡፡ ከዚህ አንጻር እንደ ሃገር የምናስመዘግባቸው ስኬቶች ለህዝባችንን እና ለአጋሮቻችን የሚሰጠው ትርጉም ትልቅ የመሆኑን ያህል ይህ ጅምር እመርታ የማያስደስታቸው በከፍተኛ የአመራር ቁርጠኝነት እና የአጋሮች ጥረት የተገኙ ውጤቶች የሚያቅራቸው ሀይላት መኖራቸው ግን ሳይታለም የተፈታ ነው፡፡
ከዚህ አንጻር በኢትዮጵያ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ በመስኖ ዘረፍ እየተገኘ ያለውን ስኬት ለመገንዘብና እውቅና ለመስጠት ሲቸገሩ ይስተዋላል፡፡ ይሁን እንጂ ሚኒስቴር መስሪያ ቤታችን ይህንን ሁኔታ ወደ ጎን በመተው የተቋቋመለትን አላማ እና የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ሉአላዊነት እና የህዝብ ጥቅም ታሳቢ በማድረግ በዘርፉ የሚገኙ አሰራሮችንና ህጎችን መሰረት በማድረግ በሃገሪቱ የጀመራቸውን በውጤት የታጀበ የመስኖ ፕሮጀክቶች የማጠናቀቅ ድሎችን አጠናክሮ የሚቀጥል ይሆናል፡፡
ለኢትዮጵያ የምግብ ሉኣላዊነት መረጋገጥ እንሰራለን!!
የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚንስቴር
ሃምሌ 9 ቀን 2018 ዓ.ም
የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስቴር
መግለጫ እነሆ ፥
#ethiopia | አገራዊ የመስኖ ልማት ጉዞ ተስፋ ሰጪ እመርታ የኢትዮጵያ በመስኖ የመልማት አቅሟን፤ ለመጠቀምና ተፈጥሮ የለገሰቻትን ውሃ፣ መሬት፣ ምቹ የአየር ሁኔታ እንደዚሁም አምራች የሰውሃይል በአግባቡ መጠቀም ባለመቻሏ ለዘመናት የራሷን የምግብ አቅርቦት እንኳን መሸፈን ሳትችልና በችግር ወቅት ለዕርዳታ ወደ ውጪ ስታማትር መኖሯ የቅርብ ጊዜ ታሪካችን ነው፡፡
ኢትዮጵያን በተለያየ ጊዜያት ያስተዳደሩ መንግስታት ምርታማነት ለማሳደግ ያስችለናል ያሏቸውን የተለያዩ ሙከራዎች በመከተል ጥረት ቢያደርጉም በሚጠበቀው ልክ ውጤታማ ሳይሆኑ ቀርተዋል፡፡ በዚህም ሳቢያ አገራችን የራሷን የምግብ አቅርቦት መሸፈን ሳትችል፣ በቢሊዮን የሚቆጠር የውጭ ምንዛሬ በማውጣት ስንዴን ጨምሮ የተለያዩ የምግብ ምርቶችን ከውጭ ስታስገባ ኖራለች።
እንደ ሃገር ሰፋፊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ከ1960ዎቹ ጀምሮ መተግበር ቢጀምሩም ቁጥራቸው እጅግ ጥቂትና ውጤታቸውም በዛው ልክ ውስን እንደነበር በመስኩ የተደረጉ የዳሰሳዎች ጥናቶች ያሳያሉ ፡፡ ለአብነትም ለስኳር ልማት የተገነቡ ፕሮጀክቶች እንደ ወንጂ፣ መተሃራ፣ ፊንጫ ፣ የአሚባራ፣ የአልዌሮ፣ የጎዴ፣ የተንዳሆ እና የከሰም መስኖ ልማት ፕሮጀክቶች ተጠቃሾች ቢሆኑም በትግበራ ሂደት ግን ለአመታት ባጋጠሙ ተግዳሮቶች ውጤታማ ሳይሆኑ መቆየታቸው ይታወቃል፡፡
ይህንን አዙሪት በመስበርና የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ፣ ከተፈጥሮ ዝናብ ባሻገር የከርሰ-ምድርና የገጸ-ምድር ውኃን በአግባቡ በመጠቀም መስኖን ማስፋፋት ወሳኝ ሆኖ ተገኝቷል። በተለይም ባለፉት የለውጥ አመታት የኢትዮጵያ መንግስት ከዚህ የተለመደና ፈተና የሆነ አዙሪት ለመላቀቅ የሚያስችሉ የተለያዩ እቅዶችን አዘጋጅቶ እና ዘርፉን ራሱን በቻለ ሚኒስቴር መስራቤት ደረጃ በማደራጀት አዲስ የፖሊሲ መር የልማት ጥረትን ተግባራዊ ለማድረግ የሚያስችል ስራ መስራት ጀምሯል፡፡
መንግስት የኢትዮጵያን የምግብ ሉአላዊነት ለማረጋገጥ ከወሰዳቸው ወሳኝ እርምጃዎች መካከል የመስኖ ልማት ዘርፍን ውጤታማ በሆነ መንገድ በማሻሻል ምርታማነትን ማሳደግ እንዲቻል ዘርፋ ለአጠቃላይ አገራዊ እድገት የሚኖረውን ሚናም በልዩ ትኩረት ለማሳደግ እንዲያስችለው መስኖ በጥናት በተለዩ ቦታዎች ላይ በልዩ ትኩረት እንዲያስፋፋ በማለም የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስቴርን በ2014 ዓ/ም እንዲቋቋም አድርጓል፡፡ በዚህም የአገር አቅም በፈቀደ ልክም መንግስት ለዘርፉ ከፍተኛ በጀት እንዲመደብለት እና በዘርፉ ተግባራዊ ለውጥ እንዲመጣ የሚያስችሉ ስራዎችን ሲሰራ ቆይቷል ፡፡
የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስቴርም የመስኖና ቆላማ አካባቢ ልማትን ወደ ተቀናጀ የልማት አቅጣጫ በመምራት፤ ሀገራችን ያላትን ከፍተኛ የውሃና ሰፊ የመሬት ሀብት ማዕከል በማድረግ፤ የመስኖ ልማትን በማስፋፋት እና በቆላማ አካባቢ የሚገኘውን እምቅ የልማት ፀጋዎችን በማጥናትና ለአርብቶአደሩና ከፊልአርብቶአደሩ ጥቅም እንዲዉል በማድርግ የሀገራችንን የምግብ ሉዓላዊነት እንዲረጋገጥ ለማስቻል መተግበር የጀመራቸውም ስራዎች አመርቂ ውጤቶች ማሳየት ጀምረዋል፡፡
መስሪያ ቤቱ ግዙፍ የመስኖ ፕሮጀክቶችን በማስጠናትና በመገንባት፤በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ እና በክልሎች የሚገቡ አነስተኛ መስኖዎችን በመከታተልና ድጋፍ በመስጠት በሃገሪቱ ምርትና ምርታማነት ላይ ተጨባጭ ለውጥ ማምጣት ያስቻሉ ተግባራትን መጀመሩም ከወዲሁ መታዘብ ይቻላል፡፡
በተለይ ደግሞ ባለፋት ሁለት የበጀት አመታት ማለትም በ2017 እና 2018 በጀት ዓመት በኢትዮጵያ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ አፈጻጸም ዙርያ የተከናወኑ ስራዎች በአጠቃላይ በዘርፋ የሚታዩ ጅምር ሙከራዎችን ወደ አዲስ ታሪክ ያሸጋገረ ምዕራፍ ላይ መድረሱን መታዘብ ይቻላል።
ዘርፋ ከተሰጠው ልዩ ትኩረትና በአገር አቀፍ ደረጃ የመስኖ ልማት ጥያቄዎች መበራከት ከጅምሩ በቂ ጥናቶችና የዲዛይን ስራዎች ጥልቅ የበጀት ዝግጅትና በከፍተኛ የህዝብና የመንግስት አመራር ማእቀፎች በቂ ውይይት ተደርጎባቸው እንዲሁም የአፈጻጸም ስጋቶችና በተለይም ከአጠቃላይ የበጀት ዝግጅቶች አንጻር በነበሩ ውስንነቶች ጉልህ ችግሮች የነበሩ ቢሆንም ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ከህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እና ከገንዘብ ሚኒስቴር ጋር በፍጥነት በመመካከር መሰረታዊ የማጣጣም ስራዎች መከወን በመቻሉ በርካታ ስራዎችን በተከታታይ ወራት በስኬት ሐዲድ ለማስጓዝ ተችሏል።
በዚህም በነዚህ ሁለት አመታት ለበርካታ አመታት ግንባታቸው የተጓተቱ ፣ የዲዛይን ስራ ጉድለቶች የነበሩባቸው ተጠናቀውም ለረጅም ጊዜ ጥገና ያልተደረገላቸው እና ከፍተኛ ብልሽት አጋጥሟቸው የነበሩ ፕሮጀክቶችን ቁርጠኛ በሆነ የፕሮጀክት አመራር ክትትል እና ጥብቅ የኮንትራት አስተዳደር ስርዓትን መሰረት በማድረግ ፕሮጀክቶችን በማጠናቀቅ አመርቂ ውጤቶች ተመዝግበዋል፡፡
ለዚህ ስኬት ሚኒስቴር መስሪያ ቤታችንም መንግስት የኢትዮጵያን የምግብ ሉአላዊነት ለማረጋገጥ ያለውን ፅኑ ፍላጎትና እያደረገ ያለውን ከፍተኛ ድጋፍ ከግንዛቤ በማስገባት ይህንንም በሚመጥን መልኩ ተገቢውን ትኩረት ሰጥቶ በጥራት በፍጥነት እና የኮንትራት ስምምነቶችን መሰረት በማድረግ የሰጠው በሳል አመራርም ተጠቃሽ ምክንያት ነው።
በዚህም ምክንያት ለአመታት የዘገዩና የማህበረሰባችን የአመታት የቅሬታ ምንጨ ሆነው የኖሩትን በአጠቃላይ 10 የሚሆኑ ግዙፍ የመስኖ ፕሮጀክቶችን በአጭር ግዜ ከውስብስብ ችግሮች በማላቀቅ በልዩ ትኩረት ቅድሚያ በተሰጣቸው አቅጣጫ መሰረት በተፋጠነ ጊዜ እንዲጠናቀቁ ጥረት ተደርጓል።
እነዚህም የመስኖ መሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች የማልማት አቅማቸው እና ተጠቃሚ የሚያደርጉት እማና አባ ወራወዎች በቅደም ተከተላቸው መሰረት የሚከተሉት ናቸው ፡-
1.ጊዳቦ ሎት 2 - የማልማት አቅሙ- 13420 ሄ/ር 26840 እማ/አባወራዎች
2. ጎዴ -የማልማት አቅሙ -10,000 ሄ/ር 20000 እማ/አባወራዎች
3. ወልመል ሎት 1 እና 2 – 12040 ሄ/ር -24080 እማ/አባወራዎች
4. ጨልጨል ሎት 2- 4145 ሄ/ር 8290 እማ/አባወራዎች
5.የቄጦ መስኖ 5000 ሄ/ር 10,000 እማ/አባወራዎች
6. የታችኛው ርብ -3200 ሄ/ር 6400 እማ/አባወራዎች
7. የተንዳሆ - 60,000 ሄ/ርያለማል 120,000 እማ/አባወራዎች
8. የከሰም መስኖ -20 ሺኅ ሄ/ር 40,000 እማ/አባወራዎች
እንዲሁም አርጆ ዲዴሳ እና መገጭ መስኖ ልማት ፕሮጀክቶች መሠረታዊ የግንባታ ሥራቸው አልቆ የማጠናቀቂያ ሥራቸው እየተፋጠነ ከመሆኑም በላይ በቅርቡ በክብር የሚመረቁ ይሆናል፡፡
መገጭ እና አርጆ የመስኖ ፕሮጀክቶች ሲጠናቀቁ በአጠቃላይ የ10ሩ ፕሮጀክቶች ብቻ ድምር የማልማት አቅማቸው 224,805 ሄክታር ሲሆን 450,000 እማና አባወራዎችን ተጠቃሚ የሚደርጉ ናቸው፡፡
በሌላ በኩል እንደ ጨልጨል (ሎት1) አጂማጫጫ፣ ካሊድ ዲጆ፣ ሎጊያ፣ ላይኛው ጉደር፣ አንገር ፣ ፈንታሌ፣ ወይቦ፣ ላይኛው ርብ፣ ሽንሌ፣ እና አደኣ በቾ የመስኖ መሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች በዕቅዳቸው መሠረት የግንባታ ስራዎቻቸው እየተከናወ ባጠናቀቅናቸው የመስኖ ፕሮጀክቶች በአሁኑ ወቅት ሰፋፊ የእርሻ መሬቶችን በማልማት የማህበረሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተቀናጁ ስራዎች በመተግበር ላይ እንገኛለን፡፡
መንግስት ለመስኖ ልማቱ ዘርፍ በሰጠው ከፍተኛ ትኩረት በተሰሩ ስራዎች ከለውጡ በፊት 490 ሺህ ሄክታር የነበረው የመስኖ ሽፋን ወደ 2.6 ሚሊዮን ሄክታር ከፍ እንዲል አድርጓል፡፡ አሁን የተጀመሩ ፕሮጀክቶችም ሲጠናቀቁ የአገራችን የመስኖ ሽፋን በከፍተኛ መጠን የሚጨምር ይሆናል፡፡ እነዚህ መሰረተ ልማቶችም የተጀመረውን የኢትዮጵያን የምግብ ሉአላዊነት በማረጋገጥ ረገድ የሚኖራቸው ሚና ከፍተኛ ነው፡፡
በ2017 እና በ2018 በጀት አመት ፕሮጀክቶች አጠናቅቀን ለስኬት ስንበቃ ፤ ግንባታዎች ባቀድነው ጊዜ እንዳይጠናቀቁ ስያደርጉ የቆዩትን፣ እንደዚሁም በቀጣይነትም ስራን ሊያስጓጉሉ የሚችሉትን ቁልፍ ማነቆዎች በጥናት በመለየት ውስብስብ ለሆኑና ለቆዩ ችግሮች ተገቢ እና ህጋዊ መፍትሄ እንዲያገኙ በማድረግ ረገድ የተሰሩ ስራዎች ሚናቸው ትልቅ ነው፡፡
በመሆኑም ይህ ፈጣን የፕሮጀክት አፈጻጸም እና ክትትል በቀላሉ የተገኘ እንዳልሆነ መገንዘብ ያሻል።
ለመሆኑ በእነዚህ የግንባታ 2 አመታት እንደማንኛውም የኮንስትራክሽን ዘርፍ የመስኖ ግንባታ ያጋጠሙት ተግዳሮቶች ምንድናቸው? የተሰጣቸው መፍትሔዎችስ ?
በግንባታ ሂደቱ ያጋጠሙንን ተጠባቂና ተጠባቂ ያልሁኑ ተግዳሮቶች ተወጥተን የግንባታ ስራችንን ስናከናውን በግንባታ ሂደቱ ላይ ተፅዕኖ ያሳደሩ ዋና ዋና ተግዳሮቶችን የሚከተሉት ናቸው፦
* የመስኖ ልማት ፕሮጀክቶች ከውኃ ጋር የተቆራኙና በካበተ የዘርፍ ጥናት የተደገፋ መሆን የሚገባቸው በመሆናቸው በዘርፉ ልምድ ያላቸው በቂ አገር በቀል የአማካሪና ተቋራጮች አቅም በበቂ አለመኖሩ ከጅምሩ የታዩ ተግዳሮቶች ነበሩ:: በተጨማሪም አብዛኞቹ ፕሮጀክቶች የሚከናወኑት በመንግስት የልማት ድርጅቶች ሲሆን ተቋማቱ በዘርፋ ለሚደረግ የመሰረተ ልማት ግንባታ የነበራቸው ልምድና አቅምም ውስን ከመሆኑም በላይ ከግሉ ዘርፍ የሚሳተፉት በጣት የሚቆጠሩ ተቋማትም ገና አጥጋቢ ቁመና ያልነበራቸው መሆኑ።
* የበጀት እጥረትና የገንዘብ አቅርቦት መዘግየት፦ ፕሮጀክቶቹ ከፍተኛ ሀብት የሚጠይቁ ቢሆንም በየዓመቱ የሚመደበው በጀት አነስተኛ መሆኑና የተፈቀደው በጀትም በወቅቱ ጥሬ ገንዘብ ሆኖ ባለመለቀቁ ከክፍያዎች መስተጓጎል የተነሱ መጓተቶችና የዋጋ ንረት ፕሮጀክቶች በሚፈለገው ደረጃ ማከናወን አለመቻሉ፣
* ከፍተኛ የገበያ የዋጋ ንረት (Market Inflation)፦ ከ2013 ዓ.ም ጀምሮ በዓለም አቀፍና አገር ውስጥ ሁኔታዎች ምክንያት እንደ ሲሚንቶ፣ ብረት፣ ነዳጅ እና የጉልበት ዋጋ ላይ በየግዜው ከፍተኛ ጭማሪ ማጋጠሙ። በዚህም ምክንያት የፕሮጀክት በዘገዩ ቁጥር ወጪዎቻቸው በየግዜው እንዲጨምሩ ምክንያት ሆነዋል ::
* የስትራቴጂካዊ ግንባታ ዕቃዎች አቅርቦት እጥረት፦ ሲሚንቶ፣ ብረትና ነዳጅ በገበያ ላይ በበቂ ሁኔታ በወቅቱ አለመገኘታቸው የግንባታውን ፍጥነት በእጅጉ ገድበውት ቆይተዋል። በዚህም ምክንያት ፕሮጀክቶች በእቅዳቸው ልክ እንዳይከወኑ ምክንያት ሆኖ ቆይቷል ::
* የግድብ እና መስኖ መሰረተ ልማቶች ዲዛይን ስራዎች ጉልህ ክፍተቶችና ያጋጠሙ የጂኦሎጂካል ውስብስብነት ችግሮች :: ምንም እንኳን ፕሮጀክቶች መነሻ የሚሆኑ ጥናትና ዲዛይን ተሠርቶባቸው ቢጀመሩም፣ በትግበራ ወቅት በሚያጋጥሙ የመሬት አቀማመጥና የጂኦሎጂካል ይዘቶች ምክንያት የዲዛይን ክለሳዎችን ማድረግ የግድ ማስፈለጉ የውል ማሻሻያዎችንና የጊዜ ማራዘሚያዎችን እንዲደረጉ የግድ የሚያስብሉ ሁኔታዎች አጋጥመዋል ::
በዚህም ምክንያት ለሚኖሩ ለውጦች ተጨማሪ የኮንትራት ወጪ እና ግዜ መጠየቃቸው የግድ ሆኗል።
የተወሰዱ ስልታዊና መዋቅራዊ የማስተካከያ እርምጃዎች የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስቴር ከዚህ በፊት በተደጋጋሚ ያጋጠሙትን የአሠራር ክፍተቶች፣ የኦዲት ግኝቶችና የባለድርሻ አካላትን አስተያየቶች እንደ ግብዓት በመውሰድ ሰፊ ተቋማዊ ለውጥ (Institutional Reform) አድርጓል።
በዚህም መሠረት የተወሰዱት ቁልፍ ተቋማዊ እርምጃዎች የሚከተሉት ናቸው፦
* ልዩ የፕሮግራም ማስተባበሪያ ጽሕፈት ቤት በአዲስ መልክ በ2017ዓ/ም ተቋቁሟል ፦ከዋናው መሥሪያ ቤት እስከ ፕሮጀክት ሳይት የነበረውን የቁጥጥር እና ክትትል ለማጥበቅና የውል አስተዳደር እንዲሁም የቁጥጥር ሥርዓቱን (Contract Administration & Construction supervision) በዲጂታል ፕላትፎርም ጭምር ለማዘመን ዘርፈ-ብዙ ብቁ ባለሙያዎችን ያቀፈ ፕሮጀክት ጽሕፈት ቤት ተቋቁሟል።
* ጥብቅ የክትትልና ግምገማ (M&E) ሥርዓት መዘርጋት፦የዲጂታል ቴክኖሎጂን በመጠቀም ዕለታዊ፣ ሳምንታዊ፣ወርሃዊ፣ ሩብ ዓመት፣ ግማሽ ዓመት እና ዓመታዊ የክትትልና የመስ ክምልከታ ሥርዓት ተዘርግቶ ተግባራዊ ሆኗል።
* በኮንትራት ስምምነት መሰረት ለፕሮጀክቶች ክትትል የሚያስፈልገውን ሎጅስቲክስ እንዲሟላ ተደርጓል፥- በአዲስ መልክ ለተደራጀዉ ፕሮግራም ጽ/ቤት ከማዕከል እስከ ፕሮጀክት ሳይት ለተመደቡ የስራ መሪዎችና ሙያተኞች የሚያስፈልጉ የመስክን ነባራዊ ሁኔታ የሚቋቋሙ የመስክ ተሽከርካሪዎች እና የቢሮ ቁሳቁሶችን በኮንትራት ስምምነት ውስጥ በተቀመጠው መሰረት በማሟላት የክትትል አመራሮች እና ባለሙያዎች በተቀናጀ መልኩ ጉልበታችዉና እውቀታቸዉን ለፕሮጀክቶቹ ስኬት የሚያውሉበትን ሁኔታ በመፍጠር በጊዜና በጥራት ፕሮጀክቶችን በማጠናቀቅ ውጤታማ ስራ እየተመዘገበ ይገኛል::
* የቁሳቁስ አቅርቦት ሰንሰለትን ማሳለጥ (Supply Chain Optimization)፦ የሲሚንቶ እና የነዳጅ እጥረትን ለመቅረፍ ሚኒስቴሩ በቀጥታ ከአምራች ፋብሪካዎችና አቅራቢዎች ጋር ስልታዊ ትስስር በመፍጠር የግንባታ ግብዓቶች ሳይቆራረጡ ፕሮጀክት ሳይት ላይ እንዲቀርቡ አድርጓል።
* ባለሦስት ወገን ስምምነት (Tri-party Agreement) መተግበር፦ በተቋራጭ፣ በአማካሪ መሐንዲስ፣ በባለቤት(ሚኒስቴሩ) እና በቁሳቁስ አቅራቢዎች መካከል የተቀናጀ የጋራ መግባቢያ ስምምነት በመፈረም ሥራዎች በተቀመጠላቸው ወሰን፣ በጀትና ጥራት ኮንትራት መሰረት አድርገው እንዲከናወኑ ተደርጓል።
* አዳዲስ መመሪያዎችና ስታንዳርዶች ማዘጋጀት፦ ወደፊት ለሚከናወኑ ማናቸውም ግንባታዎች መነሻ የሚሆኑ የፕሮጀክት አስተዳደርን የሚያዘምኑ አዳዲስ የአሠራር ደንቦችና መመሪያዎች ተዘጋጅተዋል።
* የዋጋ ማስተካከያ መፍቀድ፦ አገር በቀል ተቋራጮች ፕሮጀክቶች በወቅቱ መጠናቀቅ ባለመቻላቸው ያጋጠመውን የዋጋ ንረት በራሳቸ መቋቋም ባለመቻላቸው፣ በመንግስት የተቀመጡ አሠራሮችን በመከተል ቀደም ሲል የዋጋ ማስተካከያን ይከለክሉ የነበሩ ውሎችን ከ2013 ጀምሮ በተሰጠው የመንግስት ውሳኔ መሰረት ውሎችን በማሻሻል የዋጋ ማስተካከያ በሃገር ደረጃ እንዲደረግ ፈቅዷል።
* የበጀት እጥረትና የገንዘብ አቅርቦት መዘግየትን በተመለከተ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ከገንዘብ ሚኒስቴር ጋር በቅርበት በመወያየት እና በመስራት አስፈላጊው በጀት እና ጥሬ ገንዘብ በወቅቱ ለመስኖ ፕሮጀክቶች ቅድሚያ ተሰጥቶ እንዲለቀቁ ማድረግ ተችሏል፡፡
የመስኖ ፕሮጀክቶች እንደ ማንኛውም የግንባታ ፕሮጀክቶች መንግስት ባወጣው የግዥ መመሪያዎች፣ ደንቦች እና ውሎች የሚተዳደሩ ናቸው :: የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስቴር መ/ቤት ከሌሎች ተቋማት የተረከባቸውንም ሆነ በራሱ የጀመራቸውን ፕሮጀክቶች የሚያስተዳድረው የመንግስትን ህግና ስርአትን በማክበር በኮንትራት ውል ስምምነት መሰረት ብቻ ነው፡፡
በዚህም መሰረት በየግዜው ልዩ ፍቃድ የሚያስፈልጋቸው ጉዳዮች ሲያጋጥሙም በህግ የመፍቀድ መብት ያለውን የመንግስት አካል ፍቃድ በማግኘት ብቻ የተፈፀሙ ስራዎችን መከወን ተችሏል ፡፡
ከመስኖ ፕሮጀክቶች ውስብስብ ባህሪ በመነሳት በተቻለ መጠን ባሉ ሀገራዊ አቅሞች እና ልምድና አቅም ባላቸው አማካሪ ድርጅቶች ዝርዝር ጥናትና ዲዛይን ሳይሰራ የመስኖ ፕሮጀክቶች አይጀመሩም፡፡ ሆኖም በትግበራ ወቅት የዲዛይን ክፍተቶች መኖራቸው ሲታወቅ በተቀመጠው የውል አስተዳደር ስምምነት መሰረት የፕሮጀክቶች የዲዛይን ችግር እንዲፈታ በማድረግ የተጀመሩ ፕሮጀክቶች በዲዛይን
ማሻሻያው መሰረት እንዲቀጥሉ እና እንዲጠናቀቁ ይደረጋሉ፡፡
ምንም እንኳን የዲዛይን ክፍተቶች ችግር ደረጃ ቢለያይም ፕሮጀክቶች በተግባር የዲዛይን ክፍተቶች እንደሚያጋጥማቸው ይታወቃል፡፡ ከፕሮጀክቶች ውል አስተዳደር አንፃርም ተቋራጭ እና አማካሪ ድርጅቶች በገቡት ውል መሰረት ብቻ ሚኒስቴር መ/ቤቱ ውሎችን ያስተዳድራል በዚህም የፕሮጀክቶች አፈጻጸም ውጤትም ይህንኑ ሀቅ ያረጋግጣል። በመሆኑም በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ከውል ውጪ የሚፈፀሙ ምንንም አይነት ግዥዎችና ጭማሪዎችም የሉም።
አለማቀፍ ልምዶች እንደሚያሳዩት ማንኛውም ፕሮጀክት ተግባራዊ በሚደረግባት ወቅት በገቢያ ሁኔታ ለሚከሰቱ የዋጋ ጭማሪዎች ተገቢውን አሰራር እና ኮንትራት ስምምነትን በመከተል የሚፈቀዱ የዋጋ ማስተካከያዎችን በማድረግ ፕሮጀክቶች ተግባራዊ ይደረጋሉ፡፡
በአገራችን ከ2013 ዓ.ም. ጀምሮ በከፍተኛ ሁኔታ የግንባታ ግብአቶች በመጨመሩ፣የነዳጅ ዋጋ በከፍተኛ ሁኔታ በመጨመሩ እና በአለማቀፍ ሁኔታዎች መለዋወጥ ምክንያት የግንባታ ሴክተሩ በከፍተኛ ሁኔታ ችግር ውስጥ ገብቶ ቆይተው የነበሩ ፕሮጀክቶች በመኖራቸውም እስካሁንም ከተመሳሳይ ችግሮች ሙሉ በሙሉ ለማገገም የሚያስችል ስራ መስራትም ቀጣይ የቤት ስራችን ይሆናል፡፡
በዚህም ምክንያት አገር በቀል ተቋራጭ ድርጅቶች የተከሰተውን የግንባታ ግብአቶች ከፍተኛ የዋጋ ጭማሪ በራሳቸው መቋቋም እንዳቃታቸው መንግስት በመገንዘቡ የተቀመጡ አሰራሮችን በመከተል የዋጋ ማስተካከያ እንዲደረግ ፍቃድ ሰጥቷል፡፡ በዚህም መሰረት ቀደም ሲል የዋጋ ማስተካከያ ይከለክሉ የነበሩ ውሎችን በማሻሻል የዋጋ መስተካከያ መፍቀድ እና ተግባራዊ ማድረግ ከፕሮጀክቱ መጠናቀቅ የሚያስገኘውን ጥቅም ቅድሚያ በመስጠት በተሰጠው ፍቃድ መሰረት ተግባራዊ ተደርጓል፡፡
ኢትዮጵያ በዝናብ ጥገኝነት ላይ የተመሠረተውን የግብርና ክፍለ-ኢኮኖሚ ወደ መስኖ መርና አስተማማኝ ምርታማነት ለመቀየር የጀመረችውን ጉዞ ስኬታማ ሊሆን የሚችለው አሁን የተጀመሩት ተቋማዊ ሪፎርሞች እና ፕሮጀክቶችን በማጠናቀቅ ወደ ውጤት የመቀየር ጅምሮች ቀጣይነት ሲኖራቸው ብቻ ነው። ይህንን ለማደናቀፍና ኮንትራትና ፕሮጀክት አስተዳደር ስርዓትን በአግባቡ መረዳት ባቃታቸው ወይም ሆን ተብሎ ሂደቶችን ለማጠልሸት የሚሰሩ ስራዎች በፍፁም ተቀባይነት ሊኖራቸው አይችሉም ::
እንደሚታወቀው ሃገራችን በተለያዩ ሴክተሮች አስደናቂ የሆኑ ስኬቶችን እያስመዘገበች ትገኛለች፡፡ ከዚህ አንጻር እንደ ሃገር የምናስመዘግባቸው ስኬቶች ለህዝባችንን እና ለአጋሮቻችን የሚሰጠው ትርጉም ትልቅ የመሆኑን ያህል ይህ ጅምር እመርታ የማያስደስታቸው በከፍተኛ የአመራር ቁርጠኝነት እና የአጋሮች ጥረት የተገኙ ውጤቶች የሚያቅራቸው ሀይላት መኖራቸው ግን ሳይታለም የተፈታ ነው፡፡
ከዚህ አንጻር በኢትዮጵያ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ በመስኖ ዘረፍ እየተገኘ ያለውን ስኬት ለመገንዘብና እውቅና ለመስጠት ሲቸገሩ ይስተዋላል፡፡ ይሁን እንጂ ሚኒስቴር መስሪያ ቤታችን ይህንን ሁኔታ ወደ ጎን በመተው የተቋቋመለትን አላማ እና የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ሉአላዊነት እና የህዝብ ጥቅም ታሳቢ በማድረግ በዘርፉ የሚገኙ አሰራሮችንና ህጎችን መሰረት በማድረግ በሃገሪቱ የጀመራቸውን በውጤት የታጀበ የመስኖ ፕሮጀክቶች የማጠናቀቅ ድሎችን አጠናክሮ የሚቀጥል ይሆናል፡፡
ለኢትዮጵያ የምግብ ሉኣላዊነት መረጋገጥ እንሰራለን!!
የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚንስቴር
ሃምሌ 9 ቀን 2018 ዓ.ም
21 days ago
✨ጥርት ያለ የመዝናኛ ዓለም ቴሌስትሪም!
ያለ ዲሽና ገመድ በቴሌስትሪም ሲም እና በWi-Fi ብቻ በከፍተኛ ጥራት ይመልከቱ።
💁♂️ ከበርካታ የቲቪ ቻናል አማራጮቹ ጋር የአገር ውስጥና ዓለም አቀፍ ቻናሎች፣ ቀጥታ ሥርጭቶች በተጨማሪ እንደፍላጎትዎ የተለያዩ ምርጥ ፊልሞችን ከVOD ጋለሪው ላይ መኮምኮምም ያስችላል፡፡
👉 ቴሌቪዥንዎ ስማርት ባይሆን ቴሌስትሪም የስማርት ቲቪ አገልግሎትንም አሟልቷል፤ ቢፈልጉ ዩቲዩብ አልያም በቴሌስትሪም ውስጥ የሚገኙ መተግበሪያ ጭነው መጠቀም ይቻላል።
📍መገልገያውን በአንድ ጊዜ ወይም በረጅም ጊዜ ክፍያ፣ ከ3 ወር ነጻ የአገልግሎት ክፍያ ጋር በዘመን ገበያ ወይም ከአገልግሎት ማዕከላት ያግኙ፡፡
#telestream #ethiotelecom #nexthorizon #telebirr #telebirrsuperapp #digitalethiopia #realizingdigitalethiopia
ያለ ዲሽና ገመድ በቴሌስትሪም ሲም እና በWi-Fi ብቻ በከፍተኛ ጥራት ይመልከቱ።
💁♂️ ከበርካታ የቲቪ ቻናል አማራጮቹ ጋር የአገር ውስጥና ዓለም አቀፍ ቻናሎች፣ ቀጥታ ሥርጭቶች በተጨማሪ እንደፍላጎትዎ የተለያዩ ምርጥ ፊልሞችን ከVOD ጋለሪው ላይ መኮምኮምም ያስችላል፡፡
👉 ቴሌቪዥንዎ ስማርት ባይሆን ቴሌስትሪም የስማርት ቲቪ አገልግሎትንም አሟልቷል፤ ቢፈልጉ ዩቲዩብ አልያም በቴሌስትሪም ውስጥ የሚገኙ መተግበሪያ ጭነው መጠቀም ይቻላል።
📍መገልገያውን በአንድ ጊዜ ወይም በረጅም ጊዜ ክፍያ፣ ከ3 ወር ነጻ የአገልግሎት ክፍያ ጋር በዘመን ገበያ ወይም ከአገልግሎት ማዕከላት ያግኙ፡፡
#telestream #ethiotelecom #nexthorizon #telebirr #telebirrsuperapp #digitalethiopia #realizingdigitalethiopia
21 days ago
“ቀይ ባሕርን ያጣነው እኛ ስንጨቃጨቅ ጊዜ ጠብቀው ጣልቃ በመግባት መሻታችንን እንዳንከውን ባደረጉ ሃይሎች ነው” ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር)
ቀይ ባሕርን ያጣነው እኛ ስንጨቃጨቅ ጊዜ ጠብቀው ጣልቃ በመግባት መሻታችንን እንዳንከውን ባደረጉ ሃይሎች ነው አሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፡፡
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ጉባዔ ማስጀመሪያ መርሐ ግብር ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት ተካሂዷል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዚህ ወቅት እንዳሉት ÷ ልዩነትን በሰለጠነ መንገድ በውይይት መፍታት የሀገርን ጥቅም ለማስጠበቅና ዘላቂ ሰላምን ለማስፈን ጉልህ ሚና አለው፡፡
ስለሆነም በምክክር ጉባዔው እኛ እና ከእኛ በፊት የነበሩ ሰዎች ያጧቸውን ጉዳዮች ዳግም ልጆቻችን እንዳያጡ በታላቅ ኃላፊነት መስራት እንደሚገባ አንስተዋል፡፡
በኢትዮጵያ ውስጥ በርካታ ችግሮች መኖራቸውን ጠቁመው÷ ይህንን ችግር ወደ ዕድል መቀየር ከተቻለ የተሻለ ትውልድ መፍጠር ይቻላል፤ የምክክር ጉባዔውም ሀገርን የሚታደግና የሚገነባ ታሪክ ለመጻፍ ታላቅ ዕድል የሚሰጥ ነው ብለዋል፡፡
ባለፉት ጥቂት ዓመታት የተገኘውን እድል ሁሉ በመጠቀም በኢትዮጵያ የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚ እና የወታደራዊ ሪፎርም በማካሄድ በርካታ ውጤቶች መገኘታቸውን አስገንዝበዋል፡፡
ኢትዮጵያ የባሕር በር አልባ ሆና የጂኦግራፊ እስረኛ የሆነችበት ዋና ምክንያት ያልተመረጠ እና ያልተወያየ መንግሥት በፖለቲካ ሸፍጥና ሴራ እንዲሁም የውስጥ መከፋፈልና ስንፍና መሆኑን አብራርተዋል፡፡
ቀይ ባሕርን ያጣነው እኛ ስንጨቃጨቅ ጊዜ ጠብቀው ጣልቃ በመግባት መሻታችንን እንዳንከውን ባደረጉ ሃይሎች ነው ሲሉ አጽንኦት ሰጥተዋል፡፡
ይህ ታሪካዊ ክስተት እንደ አንድ እኩይ እሳቤ መገለጫ የሚጠቀስ ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ÷ የኢትዮጵያን መሻትና ጥቅም ማስቆም የሚችል ኃይል የለም፤ ያልተሳካልን በውስጥ ስንፍናችን እንጂ አቅም አጥተን አይደለም ብለዋል፡፡
Via FMC
ቀይ ባሕርን ያጣነው እኛ ስንጨቃጨቅ ጊዜ ጠብቀው ጣልቃ በመግባት መሻታችንን እንዳንከውን ባደረጉ ሃይሎች ነው አሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፡፡
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ጉባዔ ማስጀመሪያ መርሐ ግብር ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት ተካሂዷል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዚህ ወቅት እንዳሉት ÷ ልዩነትን በሰለጠነ መንገድ በውይይት መፍታት የሀገርን ጥቅም ለማስጠበቅና ዘላቂ ሰላምን ለማስፈን ጉልህ ሚና አለው፡፡
ስለሆነም በምክክር ጉባዔው እኛ እና ከእኛ በፊት የነበሩ ሰዎች ያጧቸውን ጉዳዮች ዳግም ልጆቻችን እንዳያጡ በታላቅ ኃላፊነት መስራት እንደሚገባ አንስተዋል፡፡
በኢትዮጵያ ውስጥ በርካታ ችግሮች መኖራቸውን ጠቁመው÷ ይህንን ችግር ወደ ዕድል መቀየር ከተቻለ የተሻለ ትውልድ መፍጠር ይቻላል፤ የምክክር ጉባዔውም ሀገርን የሚታደግና የሚገነባ ታሪክ ለመጻፍ ታላቅ ዕድል የሚሰጥ ነው ብለዋል፡፡
ባለፉት ጥቂት ዓመታት የተገኘውን እድል ሁሉ በመጠቀም በኢትዮጵያ የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚ እና የወታደራዊ ሪፎርም በማካሄድ በርካታ ውጤቶች መገኘታቸውን አስገንዝበዋል፡፡
ኢትዮጵያ የባሕር በር አልባ ሆና የጂኦግራፊ እስረኛ የሆነችበት ዋና ምክንያት ያልተመረጠ እና ያልተወያየ መንግሥት በፖለቲካ ሸፍጥና ሴራ እንዲሁም የውስጥ መከፋፈልና ስንፍና መሆኑን አብራርተዋል፡፡
ቀይ ባሕርን ያጣነው እኛ ስንጨቃጨቅ ጊዜ ጠብቀው ጣልቃ በመግባት መሻታችንን እንዳንከውን ባደረጉ ሃይሎች ነው ሲሉ አጽንኦት ሰጥተዋል፡፡
ይህ ታሪካዊ ክስተት እንደ አንድ እኩይ እሳቤ መገለጫ የሚጠቀስ ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ÷ የኢትዮጵያን መሻትና ጥቅም ማስቆም የሚችል ኃይል የለም፤ ያልተሳካልን በውስጥ ስንፍናችን እንጂ አቅም አጥተን አይደለም ብለዋል፡፡
Via FMC
22 days ago
ሀገር በምክክር እና በጋራ መግባባት ላይ ስትመሠረት ዘላቂ ሰላምና ጥንካሬ ታገኛለች
በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተጻፈው የመደመር መንግሥት መጽሐፍ ላይ ሀገር በምክክር እና በጋራ መግባባት ላይ ስትመሠረት ዘላቂ ሰላምና ጥንካሬ እንደምታገኝ በሰፊው ተብራርቷል።
መጽሐፉ የኢትዮጵያን ዘመናት ያስቆጠሩ የፖለቲካ እና የማኅበራዊ ስብራቶች ለመጠገን ቁልፍ መፍትሔው ንግግርና ብሔራዊ ምክክር መሆኑን ያስረዳል።
በሀገራችን የፖለቲካ ታሪክ ውስጥ ትልቁ ጉድለት በዋና ዋና ብሔራዊ ጉዳዮች ላይ ተቀምጦ በሰለጠነ መንገድ የመመካከር ባህል ማነስ ነው።
ይህንን ክፍተት ተንተርሶ የተጻፈውና የመደመር ፍልስፍናን ወደ ተግባራዊ የመንግሥት መዋቅር የሚያሸጋግረው የመደመር መንግሥት መጽሐፍ፣ ሀገር ሊጸና የሚችለው በምክክርና በጋራ መግባባት ብቻ መሆኑን ቁልጭ አድርጎ ያሳያል።
መጽሐፉ እንደሚያስረዳው፣ ሀገራዊ ምክክር የተለያዩ ሐሳቦች በአንድ መድረክ ቀርበው፣ በውይይት ጎልብተው፣ አሰባሳቢና አስማሚ ሆነው የሚወጡበት ታላቅ ምኅዳር ነው።
በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ በሀገረ መንግሥት ግንባታ ሂደት ላይ ሕዝብ በሰፊው ተመካክሮ የጋራ መግባባት ላይ ያልደረሰባቸው በርካታ ጉዳዮች አሉ።
በዚህም የተነሣ በየዘመናቱ ቅሬታዎች፣ ኩርፊያዎች፣ አብዮቶችና ደም አፋሳሽ ግጭቶች ሲከሰቱ ኖረዋል።
የመደመር መንግሥት መጽሐፍ እንደሚያብራራው፣ ሀገራዊ ምክክር እነዚህን የዘመናት ስብራቶች ለመጠገንና አዲስ የሰላም ምዕራፍ ለመክፈት ብቸኛው አስተማማኝ መንገድ ነው።
መጽሐፉ የፖለቲካ ባህላችንን ከጠብመንጃና ከኃይል አማራጭ ወደ ጠረጴዛ ዙሪያ ንግግር መቀየር እንዳለብን ያሳስባል።
የተግባባንባቸውን ጉዳዮች በሕግና በሥርዓት አጽንቶ መጓዝ፣ ያልተግባባንባቸውን ደግሞ ለቀጣይ ምክክሮች አቆይቶ በሂደት መፍታት የሰለጠነ ማኅበረሰብ መገለጫ ነው።
ምክክር በሌለበት ምኅዳር ውስጥ ነገሮች በተናጠል ስለሚቀርቡ ለፖለቲካ ነጋዴዎች ምቹ ሁኔታን እንደሚፈጥርና ሁለንተናዊ ዕይታን እንደሚያጠፋ መጽሐፉ ያስጠነቅቃል።
ኢትዮጵያ በታላላቅ ብሔራዊ አጀንዳዎች ላይ የውስጥ አንድነትና የጋራ አቋም ሊኖራት የሚችለው ዜጎችና የፖለቲካ ኃይሎች በጋራ መድረክ ላይ ሲመክሩ ብቻ ነው።
እንደ ሀገር በአንድነት ካልቆምን የትኛውም ዓይነት የልማትም ሆነ የዲፕሎማሲ ሥራ ውጤታማ ሊሆን እንደማይችል መጽሐፉ በምክንያት ያስረዳል።
ምክክሩም የትኛውም ዜጋ ሳይገለል የራሱን ሐሳብ አዋጥቶ የጋራ ሀገር የሚገነባበትን ዕድል ይሰጣል።
በአጠቃላይ የመደመር መንግሥት መጽሐፍ እንደሚያስረዳው፣ የሀገር ጽናት የሚለካው በኃይል ሳይሆን በውስጥ መግባባት ጥልቀት ነው።
ልዩነቶችን በውይይት በመፍታት፣ የተግባባንበትን የጋራ ትርክት በማስፋትና ያልተስማማንበትን በሂደት በማጥበብ ብቻ ጠንካራና የማይናወጥ ሀገረ መንግሥት መገንባት ይቻላል።
በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተጻፈው የመደመር መንግሥት መጽሐፍ ላይ ሀገር በምክክር እና በጋራ መግባባት ላይ ስትመሠረት ዘላቂ ሰላምና ጥንካሬ እንደምታገኝ በሰፊው ተብራርቷል።
መጽሐፉ የኢትዮጵያን ዘመናት ያስቆጠሩ የፖለቲካ እና የማኅበራዊ ስብራቶች ለመጠገን ቁልፍ መፍትሔው ንግግርና ብሔራዊ ምክክር መሆኑን ያስረዳል።
በሀገራችን የፖለቲካ ታሪክ ውስጥ ትልቁ ጉድለት በዋና ዋና ብሔራዊ ጉዳዮች ላይ ተቀምጦ በሰለጠነ መንገድ የመመካከር ባህል ማነስ ነው።
ይህንን ክፍተት ተንተርሶ የተጻፈውና የመደመር ፍልስፍናን ወደ ተግባራዊ የመንግሥት መዋቅር የሚያሸጋግረው የመደመር መንግሥት መጽሐፍ፣ ሀገር ሊጸና የሚችለው በምክክርና በጋራ መግባባት ብቻ መሆኑን ቁልጭ አድርጎ ያሳያል።
መጽሐፉ እንደሚያስረዳው፣ ሀገራዊ ምክክር የተለያዩ ሐሳቦች በአንድ መድረክ ቀርበው፣ በውይይት ጎልብተው፣ አሰባሳቢና አስማሚ ሆነው የሚወጡበት ታላቅ ምኅዳር ነው።
በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ በሀገረ መንግሥት ግንባታ ሂደት ላይ ሕዝብ በሰፊው ተመካክሮ የጋራ መግባባት ላይ ያልደረሰባቸው በርካታ ጉዳዮች አሉ።
በዚህም የተነሣ በየዘመናቱ ቅሬታዎች፣ ኩርፊያዎች፣ አብዮቶችና ደም አፋሳሽ ግጭቶች ሲከሰቱ ኖረዋል።
የመደመር መንግሥት መጽሐፍ እንደሚያብራራው፣ ሀገራዊ ምክክር እነዚህን የዘመናት ስብራቶች ለመጠገንና አዲስ የሰላም ምዕራፍ ለመክፈት ብቸኛው አስተማማኝ መንገድ ነው።
መጽሐፉ የፖለቲካ ባህላችንን ከጠብመንጃና ከኃይል አማራጭ ወደ ጠረጴዛ ዙሪያ ንግግር መቀየር እንዳለብን ያሳስባል።
የተግባባንባቸውን ጉዳዮች በሕግና በሥርዓት አጽንቶ መጓዝ፣ ያልተግባባንባቸውን ደግሞ ለቀጣይ ምክክሮች አቆይቶ በሂደት መፍታት የሰለጠነ ማኅበረሰብ መገለጫ ነው።
ምክክር በሌለበት ምኅዳር ውስጥ ነገሮች በተናጠል ስለሚቀርቡ ለፖለቲካ ነጋዴዎች ምቹ ሁኔታን እንደሚፈጥርና ሁለንተናዊ ዕይታን እንደሚያጠፋ መጽሐፉ ያስጠነቅቃል።
ኢትዮጵያ በታላላቅ ብሔራዊ አጀንዳዎች ላይ የውስጥ አንድነትና የጋራ አቋም ሊኖራት የሚችለው ዜጎችና የፖለቲካ ኃይሎች በጋራ መድረክ ላይ ሲመክሩ ብቻ ነው።
እንደ ሀገር በአንድነት ካልቆምን የትኛውም ዓይነት የልማትም ሆነ የዲፕሎማሲ ሥራ ውጤታማ ሊሆን እንደማይችል መጽሐፉ በምክንያት ያስረዳል።
ምክክሩም የትኛውም ዜጋ ሳይገለል የራሱን ሐሳብ አዋጥቶ የጋራ ሀገር የሚገነባበትን ዕድል ይሰጣል።
በአጠቃላይ የመደመር መንግሥት መጽሐፍ እንደሚያስረዳው፣ የሀገር ጽናት የሚለካው በኃይል ሳይሆን በውስጥ መግባባት ጥልቀት ነው።
ልዩነቶችን በውይይት በመፍታት፣ የተግባባንበትን የጋራ ትርክት በማስፋትና ያልተስማማንበትን በሂደት በማጥበብ ብቻ ጠንካራና የማይናወጥ ሀገረ መንግሥት መገንባት ይቻላል።
22 days ago
"ከስፔን ያየነው እጅግ አስደናቂ እና አእምሮን የሚገዛ የሜዳ ላይ እንቅስቃሴ ነው። እኔ ነገሩን ወደምወደው ርዕስ፣ ማለትም ወደ ዳር ተከላካዮች (full-backs) ልመልሰው፤ በሁለቱ ቡድኖች መካከል የነበረውን ትልቁን ልዩነት በነዚሁ የዳር ተከላካዮች የሜዳ ላይ ውሎ በሚገባ መግለጽ ይቻላል። [ፔድሮ] ፖሮ እና [ማርክ] ኩኩሬላ የፈረንሳይ የመስመር ተጫዋቾችን በመቆጣጠር ረገድ እጅግ አስገራሚ ብቃት አሳይተዋል፤ በሌላ በኩል ሉካስ ዲኜ በላሚን ያማል ክፉኛ ሲፈተን እና ሲንገላታ ነበር። ከጨዋታው በፊት [ያማል] እንደዚህ ባሉ ታላላቅ እና ወሳኝ መድረኮች ላይ ብቃቱን ሊያሳይ ይችላል ወይ ብለን ተወያይተን ነበር፤ ዛሬ ግን በተግባር አረጋግጦልናል። ሁላችንም ፈረንሳይ ታሸንፋለች የሚል ግምት ስለነበረን እዚህ በመጠኑም ቢሆን ድንጋጤ ውስጥ ገብተናል፤ ምክንያቱም ፈረንሳዮች በስፔን ሙሉ በሙሉ ተጠራርገው ነው የወጡት።"
- ጋሪ ኔቪል (የቀድሞ የእንግሊዝ ብሄራዊ ቡድን ተከላካይ)
- ጋሪ ኔቪል (የቀድሞ የእንግሊዝ ብሄራዊ ቡድን ተከላካይ)
Sponsored by
Surafel
24 days ago
የከተማ አስተዳደሩ የመኖሪያ ቤት ኪራይ ቁጥጥር እና አስተዳደር አዋጅ ለአከራዩች የሰጠዉን መብት ግምት ዉስጥ እንዲያስገባ ተጠየቀ
በተከራይ እና በአከራይ መካከል የሚኖርን ሰላማዊ ግንኙነት ታሳቢ ያደረገ ስርአት እንዲኖርም ተጠይቋል።
የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 4ኛ መደበኛ ጉባኤ ከዛሬ ሐምሌ 05/2018 ዓ.ም ጀምሮ ማካሄድ ጀምሯል።
በጉባኤው ከንቲባ አዳነች አቤቤ የአስተዳደራቸውን የ2018 በጀት ዓመት የዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት አቅርበዋል። ሪፖርቱን ተከትሎ የምክር ቤት አባላት ምላሽ እና ማብራሪያ ያስፈልጓቸዋል ያሏቸዉን ጥያቄዎች አንስተዋል።
የምክር ቤት አባሉ ዶ/ር ሲሳይ መንግስቴ መኖሪያ ቤት ኪራይ ቁጥጥር እና አስተዳደር ዙሪያ ያሉ ክፍተቶችን የተመለከተ ጥያቄ አቅርበዋል።
ዶ/ር ሲሳይ "አዋጁ ክፍተቶች ያሉት ይመስለኛል። በፍጥነት የወጣ በመሆኑ የአከራዩንም ሆነ የተከራዩን ህብረተሰቡን ፍላጎት በማገናዘብ አማካኝ የሆነ ነገር ይዞ መቷል ብዬ አላምንም" ብለዋል።
መሻሻል የነበረባቸው ጉዳዩች ያሉ ቢሆንም ስልጣኑ የፌደራል መንግስት ስለሆነ ብዙ ልንል ባንችልም ያሉት ዶ/ር ሲሳይ፤ አፈፃፀሙ ግን በደንብ መታየት ያለበት ነገር መሆኑን ማንሳት አለብን ሲሉ ለምክር ቤቱ ገልፀዋል።
የምክር ቤት አባሉ በቀረበዉ ሪፖርት መሠረት 5 መቶ ሺህ የአከራይ ተከራይ ዉል ተደርጓል የሚለዉን በማስታወስ ይህ 5 መቶ ሺህ አባወራ አለ እንደማለት መሆኑን ይገልፃሉ።
"ይህ 5 መቶ ሺህ አባወራ በስሩ አራት ሰዉ አለ ብንል ሁለት ሚሊዮን ህዝብ ማለት ነዉ፤ እያወራን ያለነዉ ስለዚህ ህዝብ ነዉ ትኩረት ሰጥተን ማየት አለብን" ብለዋል።
የመኖሪያ ቤት ኪራይ ቁጥጥር እና አስተዳደር አዋጅ በየአመቱ የኪራይ መጠን እየተጠና ሊጨምር እንደሚችል ያስቀምጣል።
ዶ/ር ሲሳይ ይህንን በማስታወስ" ዘንድሮ ተጠንቶ ቀረበ የተባለዉ ጭማሪ በሁለት አመቱ ነዉ፤ አዋጁ እንኳን ለአከራዩች የሰጠዉን መብት እኛ እየነፈግን ነዉ።" ሲሉ አስረድተዋል።
ይህ የሚመለከተው የቤቶች ልማት እና አስተዳደር ቢሮ ጥናቱን በየአመቱ መስራት ይገባዋል ሲሉም አክለዋል።
አሁን ለዚህ በጀት አመት ተሰራ የተባለዉ ጥናት ምን ያህል መሠረታዊ ችግርን ይፈታል ወይ? የሚል ሀሳብ አለኝ ሲሉም ጠይቀዋል።
የማዕከላዊ ስታስቲክስ አገልግሎት በየአመቱ ከኑሮ ዉድነት እና የዋጋ ጭማሪዎች ጋር አያይዞ የሚያወጣዉን ጥናት መሠረት አድርጎ ሌላ ጥናት ሳያስፈልግ ጭማሪውን መወሠን ይቻላል ያሉት ዶ/ር ሲሳይ ለሌላ ጥናት ሀብት ማባከን አያስፈልግም ይላሉ።
ከተማ አስተዳደሩ ስለ ተከራዩች ብቻ ሳይሆን የአከራዩችን መብት ግምት ዉስጥ ማስገባት ይኖርበታል ተብሏል።
ለምክር ቤት አባሉ "አሁን ላይ በሁለት አመት ነዉ እያሰብን ያለነዉ ፤ አንድ አመት በዝምታ ነዉ የታለፈዉ ያ ማለት የአከራዩን መብት ከአዋጁ አንፃር የሚጥስ ነዉ" ሲሉ ገልጸዋል።
በምክር ቤቱ አባላት ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽ የሰጡት የቤቶች ልማት እና አስተዳደር ሀላፊ ወ/ሮ ቅድስት ወ/ጊዩርጊስ የስታትስቲክስ አገልግሎት ጥናት የሀገር አቀፍ ጥናት በመሆኑ ለከተማዉ ቤቶች ጥናቱን ለዋጋ ጭማሪ መሠረት በማድረግ መጠቀም አንችልም ብለዋል።
የከተማዋ አስተዳደሩ በዚህ አመት ለኪራይ ዋጋ ጭማሪ ያስጠናዉ ጥናት የስታቲስቲክስ አገልግሎት ያስጠናዉንም ያካተተ መሆኑን በመግለፅ ለሁለቱም አካላት እኩል ሊጠቅም የሚችል ነዉ ብለዋል።
Seledadotio
Seledadotio
በተከራይ እና በአከራይ መካከል የሚኖርን ሰላማዊ ግንኙነት ታሳቢ ያደረገ ስርአት እንዲኖርም ተጠይቋል።
የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 4ኛ መደበኛ ጉባኤ ከዛሬ ሐምሌ 05/2018 ዓ.ም ጀምሮ ማካሄድ ጀምሯል።
በጉባኤው ከንቲባ አዳነች አቤቤ የአስተዳደራቸውን የ2018 በጀት ዓመት የዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት አቅርበዋል። ሪፖርቱን ተከትሎ የምክር ቤት አባላት ምላሽ እና ማብራሪያ ያስፈልጓቸዋል ያሏቸዉን ጥያቄዎች አንስተዋል።
የምክር ቤት አባሉ ዶ/ር ሲሳይ መንግስቴ መኖሪያ ቤት ኪራይ ቁጥጥር እና አስተዳደር ዙሪያ ያሉ ክፍተቶችን የተመለከተ ጥያቄ አቅርበዋል።
ዶ/ር ሲሳይ "አዋጁ ክፍተቶች ያሉት ይመስለኛል። በፍጥነት የወጣ በመሆኑ የአከራዩንም ሆነ የተከራዩን ህብረተሰቡን ፍላጎት በማገናዘብ አማካኝ የሆነ ነገር ይዞ መቷል ብዬ አላምንም" ብለዋል።
መሻሻል የነበረባቸው ጉዳዩች ያሉ ቢሆንም ስልጣኑ የፌደራል መንግስት ስለሆነ ብዙ ልንል ባንችልም ያሉት ዶ/ር ሲሳይ፤ አፈፃፀሙ ግን በደንብ መታየት ያለበት ነገር መሆኑን ማንሳት አለብን ሲሉ ለምክር ቤቱ ገልፀዋል።
የምክር ቤት አባሉ በቀረበዉ ሪፖርት መሠረት 5 መቶ ሺህ የአከራይ ተከራይ ዉል ተደርጓል የሚለዉን በማስታወስ ይህ 5 መቶ ሺህ አባወራ አለ እንደማለት መሆኑን ይገልፃሉ።
"ይህ 5 መቶ ሺህ አባወራ በስሩ አራት ሰዉ አለ ብንል ሁለት ሚሊዮን ህዝብ ማለት ነዉ፤ እያወራን ያለነዉ ስለዚህ ህዝብ ነዉ ትኩረት ሰጥተን ማየት አለብን" ብለዋል።
የመኖሪያ ቤት ኪራይ ቁጥጥር እና አስተዳደር አዋጅ በየአመቱ የኪራይ መጠን እየተጠና ሊጨምር እንደሚችል ያስቀምጣል።
ዶ/ር ሲሳይ ይህንን በማስታወስ" ዘንድሮ ተጠንቶ ቀረበ የተባለዉ ጭማሪ በሁለት አመቱ ነዉ፤ አዋጁ እንኳን ለአከራዩች የሰጠዉን መብት እኛ እየነፈግን ነዉ።" ሲሉ አስረድተዋል።
ይህ የሚመለከተው የቤቶች ልማት እና አስተዳደር ቢሮ ጥናቱን በየአመቱ መስራት ይገባዋል ሲሉም አክለዋል።
አሁን ለዚህ በጀት አመት ተሰራ የተባለዉ ጥናት ምን ያህል መሠረታዊ ችግርን ይፈታል ወይ? የሚል ሀሳብ አለኝ ሲሉም ጠይቀዋል።
የማዕከላዊ ስታስቲክስ አገልግሎት በየአመቱ ከኑሮ ዉድነት እና የዋጋ ጭማሪዎች ጋር አያይዞ የሚያወጣዉን ጥናት መሠረት አድርጎ ሌላ ጥናት ሳያስፈልግ ጭማሪውን መወሠን ይቻላል ያሉት ዶ/ር ሲሳይ ለሌላ ጥናት ሀብት ማባከን አያስፈልግም ይላሉ።
ከተማ አስተዳደሩ ስለ ተከራዩች ብቻ ሳይሆን የአከራዩችን መብት ግምት ዉስጥ ማስገባት ይኖርበታል ተብሏል።
ለምክር ቤት አባሉ "አሁን ላይ በሁለት አመት ነዉ እያሰብን ያለነዉ ፤ አንድ አመት በዝምታ ነዉ የታለፈዉ ያ ማለት የአከራዩን መብት ከአዋጁ አንፃር የሚጥስ ነዉ" ሲሉ ገልጸዋል።
በምክር ቤቱ አባላት ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽ የሰጡት የቤቶች ልማት እና አስተዳደር ሀላፊ ወ/ሮ ቅድስት ወ/ጊዩርጊስ የስታትስቲክስ አገልግሎት ጥናት የሀገር አቀፍ ጥናት በመሆኑ ለከተማዉ ቤቶች ጥናቱን ለዋጋ ጭማሪ መሠረት በማድረግ መጠቀም አንችልም ብለዋል።
የከተማዋ አስተዳደሩ በዚህ አመት ለኪራይ ዋጋ ጭማሪ ያስጠናዉ ጥናት የስታቲስቲክስ አገልግሎት ያስጠናዉንም ያካተተ መሆኑን በመግለፅ ለሁለቱም አካላት እኩል ሊጠቅም የሚችል ነዉ ብለዋል።
Seledadotio
Seledadotio
24 days ago
የከተማ አስተዳደሩ የመኖሪያ ቤት ኪራይ ቁጥጥር እና አስተዳደር አዋጅ ለአከራዩች የሰጠዉን መብት ግምት ዉስጥ እንዲያስገባ ተጠየቀ
በተከራይ እና በአከራይ መካከል የሚኖርን ሰላማዊ ግንኙነት ታሳቢ ያደረገ ስርአት እንዲኖርም ተጠይቋል።
የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 4ኛ መደበኛ ጉባኤ ከዛሬ ሐምሌ 05/2018 ዓ.ም ጀምሮ ማካሄድ ጀምሯል።
በጉባኤው ከንቲባ አዳነች አቤቤ የአስተዳደራቸውን የ2018 በጀት ዓመት የዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት አቅርበዋል። ሪፖርቱን ተከትሎ የምክር ቤት አባላት ምላሽ እና ማብራሪያ ያስፈልጓቸዋል ያሏቸዉን ጥያቄዎች አንስተዋል።
የምክር ቤት አባሉ ዶ/ር ሲሳይ መንግስቴ መኖሪያ ቤት ኪራይ ቁጥጥር እና አስተዳደር ዙሪያ ያሉ ክፍተቶችን የተመለከተ ጥያቄ አቅርበዋል።
ዶ/ር ሲሳይ "አዋጁ ክፍተቶች ያሉት ይመስለኛል። በፍጥነት የወጣ በመሆኑ የአከራዩንም ሆነ የተከራዩን ህብረተሰቡን ፍላጎት በማገናዘብ አማካኝ የሆነ ነገር ይዞ መቷል ብዬ አላምንም" ብለዋል።
መሻሻል የነበረባቸው ጉዳዩች ያሉ ቢሆንም ስልጣኑ የፌደራል መንግስት ስለሆነ ብዙ ልንል ባንችልም ያሉት ዶ/ር ሲሳይ፤ አፈፃፀሙ ግን በደንብ መታየት ያለበት ነገር መሆኑን ማንሳት አለብን ሲሉ ለምክር ቤቱ ገልፀዋል።
የምክር ቤት አባሉ በቀረበዉ ሪፖርት መሠረት 5 መቶ ሺህ የአከራይ ተከራይ ዉል ተደርጓል የሚለዉን በማስታወስ ይህ 5 መቶ ሺህ አባወራ አለ እንደማለት መሆኑን ይገልፃሉ።
"ይህ 5 መቶ ሺህ አባወራ በስሩ አራት ሰዉ አለ ብንል ሁለት ሚሊዮን ህዝብ ማለት ነዉ፤ እያወራን ያለነዉ ስለዚህ ህዝብ ነዉ ትኩረት ሰጥተን ማየት አለብን" ብለዋል።
የመኖሪያ ቤት ኪራይ ቁጥጥር እና አስተዳደር አዋጅ በየአመቱ የኪራይ መጠን እየተጠና ሊጨምር እንደሚችል ያስቀምጣል።
ዶ/ር ሲሳይ ይህንን በማስታወስ" ዘንድሮ ተጠንቶ ቀረበ የተባለዉ ጭማሪ በሁለት አመቱ ነዉ፤ አዋጁ እንኳን ለአከራዩች የሰጠዉን መብት እኛ እየነፈግን ነዉ።" ሲሉ አስረድተዋል።
ይህ የሚመለከተው የቤቶች ልማት እና አስተዳደር ቢሮ ጥናቱን በየአመቱ መስራት ይገባዋል ሲሉም አክለዋል።
አሁን ለዚህ በጀት አመት ተሰራ የተባለዉ ጥናት ምን ያህል መሠረታዊ ችግርን ይፈታል ወይ? የሚል ሀሳብ አለኝ ሲሉም ጠይቀዋል።
የማዕከላዊ ስታስቲክስ አገልግሎት በየአመቱ ከኑሮ ዉድነት እና የዋጋ ጭማሪዎች ጋር አያይዞ የሚያወጣዉን ጥናት መሠረት አድርጎ ሌላ ጥናት ሳያስፈልግ ጭማሪውን መወሠን ይቻላል ያሉት ዶ/ር ሲሳይ ለሌላ ጥናት ሀብት ማባከን አያስፈልግም ይላሉ።
ከተማ አስተዳደሩ ስለ ተከራዩች ብቻ ሳይሆን የአከራዩችን መብት ግምት ዉስጥ ማስገባት ይኖርበታል ተብሏል።
ለምክር ቤት አባሉ "አሁን ላይ በሁለት አመት ነዉ እያሰብን ያለነዉ ፤ አንድ አመት በዝምታ ነዉ የታለፈዉ ያ ማለት የአከራዩን መብት ከአዋጁ አንፃር የሚጥስ ነዉ" ሲሉ ገልጸዋል።
በምክር ቤቱ አባላት ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽ የሰጡት የቤቶች ልማት እና አስተዳደር ሀላፊ ወ/ሮ ቅድስት ወ/ጊዩርጊስ የስታትስቲክስ አገልግሎት ጥናት የሀገር አቀፍ ጥናት በመሆኑ ለከተማዉ ቤቶች ጥናቱን ለዋጋ ጭማሪ መሠረት በማድረግ መጠቀም አንችልም ብለዋል።
የከተማዋ አስተዳደሩ በዚህ አመት ለኪራይ ዋጋ ጭማሪ ያስጠናዉ ጥናት የስታቲስቲክስ አገልግሎት ያስጠናዉንም ያካተተ መሆኑን በመግለፅ ለሁለቱም አካላት እኩል ሊጠቅም የሚችል ነዉ ብለዋል።
ቁምነገር አየለ
በተከራይ እና በአከራይ መካከል የሚኖርን ሰላማዊ ግንኙነት ታሳቢ ያደረገ ስርአት እንዲኖርም ተጠይቋል።
የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 4ኛ መደበኛ ጉባኤ ከዛሬ ሐምሌ 05/2018 ዓ.ም ጀምሮ ማካሄድ ጀምሯል።
በጉባኤው ከንቲባ አዳነች አቤቤ የአስተዳደራቸውን የ2018 በጀት ዓመት የዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት አቅርበዋል። ሪፖርቱን ተከትሎ የምክር ቤት አባላት ምላሽ እና ማብራሪያ ያስፈልጓቸዋል ያሏቸዉን ጥያቄዎች አንስተዋል።
የምክር ቤት አባሉ ዶ/ር ሲሳይ መንግስቴ መኖሪያ ቤት ኪራይ ቁጥጥር እና አስተዳደር ዙሪያ ያሉ ክፍተቶችን የተመለከተ ጥያቄ አቅርበዋል።
ዶ/ር ሲሳይ "አዋጁ ክፍተቶች ያሉት ይመስለኛል። በፍጥነት የወጣ በመሆኑ የአከራዩንም ሆነ የተከራዩን ህብረተሰቡን ፍላጎት በማገናዘብ አማካኝ የሆነ ነገር ይዞ መቷል ብዬ አላምንም" ብለዋል።
መሻሻል የነበረባቸው ጉዳዩች ያሉ ቢሆንም ስልጣኑ የፌደራል መንግስት ስለሆነ ብዙ ልንል ባንችልም ያሉት ዶ/ር ሲሳይ፤ አፈፃፀሙ ግን በደንብ መታየት ያለበት ነገር መሆኑን ማንሳት አለብን ሲሉ ለምክር ቤቱ ገልፀዋል።
የምክር ቤት አባሉ በቀረበዉ ሪፖርት መሠረት 5 መቶ ሺህ የአከራይ ተከራይ ዉል ተደርጓል የሚለዉን በማስታወስ ይህ 5 መቶ ሺህ አባወራ አለ እንደማለት መሆኑን ይገልፃሉ።
"ይህ 5 መቶ ሺህ አባወራ በስሩ አራት ሰዉ አለ ብንል ሁለት ሚሊዮን ህዝብ ማለት ነዉ፤ እያወራን ያለነዉ ስለዚህ ህዝብ ነዉ ትኩረት ሰጥተን ማየት አለብን" ብለዋል።
የመኖሪያ ቤት ኪራይ ቁጥጥር እና አስተዳደር አዋጅ በየአመቱ የኪራይ መጠን እየተጠና ሊጨምር እንደሚችል ያስቀምጣል።
ዶ/ር ሲሳይ ይህንን በማስታወስ" ዘንድሮ ተጠንቶ ቀረበ የተባለዉ ጭማሪ በሁለት አመቱ ነዉ፤ አዋጁ እንኳን ለአከራዩች የሰጠዉን መብት እኛ እየነፈግን ነዉ።" ሲሉ አስረድተዋል።
ይህ የሚመለከተው የቤቶች ልማት እና አስተዳደር ቢሮ ጥናቱን በየአመቱ መስራት ይገባዋል ሲሉም አክለዋል።
አሁን ለዚህ በጀት አመት ተሰራ የተባለዉ ጥናት ምን ያህል መሠረታዊ ችግርን ይፈታል ወይ? የሚል ሀሳብ አለኝ ሲሉም ጠይቀዋል።
የማዕከላዊ ስታስቲክስ አገልግሎት በየአመቱ ከኑሮ ዉድነት እና የዋጋ ጭማሪዎች ጋር አያይዞ የሚያወጣዉን ጥናት መሠረት አድርጎ ሌላ ጥናት ሳያስፈልግ ጭማሪውን መወሠን ይቻላል ያሉት ዶ/ር ሲሳይ ለሌላ ጥናት ሀብት ማባከን አያስፈልግም ይላሉ።
ከተማ አስተዳደሩ ስለ ተከራዩች ብቻ ሳይሆን የአከራዩችን መብት ግምት ዉስጥ ማስገባት ይኖርበታል ተብሏል።
ለምክር ቤት አባሉ "አሁን ላይ በሁለት አመት ነዉ እያሰብን ያለነዉ ፤ አንድ አመት በዝምታ ነዉ የታለፈዉ ያ ማለት የአከራዩን መብት ከአዋጁ አንፃር የሚጥስ ነዉ" ሲሉ ገልጸዋል።
በምክር ቤቱ አባላት ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽ የሰጡት የቤቶች ልማት እና አስተዳደር ሀላፊ ወ/ሮ ቅድስት ወ/ጊዩርጊስ የስታትስቲክስ አገልግሎት ጥናት የሀገር አቀፍ ጥናት በመሆኑ ለከተማዉ ቤቶች ጥናቱን ለዋጋ ጭማሪ መሠረት በማድረግ መጠቀም አንችልም ብለዋል።
የከተማዋ አስተዳደሩ በዚህ አመት ለኪራይ ዋጋ ጭማሪ ያስጠናዉ ጥናት የስታቲስቲክስ አገልግሎት ያስጠናዉንም ያካተተ መሆኑን በመግለፅ ለሁለቱም አካላት እኩል ሊጠቅም የሚችል ነዉ ብለዋል።
ቁምነገር አየለ
Comments