1 month ago
''የኡጋዱጉ አዛዥ ኢብራሂም ትራኦሬ ሰላም አምጥቷል''ሊቀመንበር ኤቫሪስቴ
#ethiopia | የቡሩንዲ ፕሬዝዳንት እና የወቅቱ የአፍሪካ ሕብረት ሊቀመንበር ኤቫሪስቴ ንዳይሺሚዬ በኡጋዱጉ ባደረጉት ይፋዊ የሥራ ጉብኝት፣ ከቡርኪና ፋሶው መሪ ኢብራሂም ትራኦሬ ጋር በወቅታዊና ቀጣናዊ ጉዳዮች ላይ መክረዋል። ይህ ስብሰባ በተለይ በሕብረቱ እና በታገዱት የሳሕል ቀጣና ሀገራት መካከል ያለውን ግንኙነት ለማደስ አዲስ ተስፋ የፈነጠቀ ሆኗል።
ፕሬዝዳንት ንዳይሺሚዬ፣ መሪው ኢብራሂም ትራኦሬ ለሀገራዊ ሰላምና መረጋጋት እያሳዩት ያለውን "ጽኑ ቁርጠኝነት" በማድነቅ የእንኳን ደስ አለዎት መልዕክት አስተላልፈዋል።
ሊቀመንበሩ ስለ ሳሕል ቀጣና እና ስለ ቡርኪና ፋሶ ህዝብ ነባራዊ ሁኔታ ካለባቸው የተዛባ ግንዛቤ ወጥተው፣ አሁን "ተጨባጭ እውነታውን" በተሻለ ሁኔታ መረዳታቸውን ገልጸዋል።
ወደ የጋራ መጻኢ እድል በጋራ ለመጓዝ የሚያስችል፣ ሀቀኛ እና በነባራዊ ሁኔታ ላይ የተመሠረተ ሪፖርት ለአፍሪካ ሕብረት ለማቅረብ ማቀዳቸውን ይፋ አድርገዋል።
ይህ ጉብኝት በዋናነት በአሁኑ ወቅት ከአባልነታቸው የታገዱት የሳሕል ሀገራት ከሕብረቱ ጋር ዳግም የሚገናኙበትን "የትብብር ድልድይ" ለመገንባትና ለማጠናከር ያለመ ነው። የቡሩንዲ ፕሬዝዳንት ጽሕፈት ቤት እንደገለጸው፣ ውይይቱ በቀጣናው ዘላቂ ሰላም ለማምጣት የሚደረገው ጥረት አካል ነው።
የስፑትኒክ ዘገባ እንደሚያመለክተው፣ ይህ ዲፕሎማሲያዊ እንቅስቃሴ በቡርኪና ፋሶ እና በጎረቤቶቿ ላይ የሚታየውን ጫና ለማርገብ ትልቅ ፋይዳ ሊኖረው ይችላል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን) #getutemesgen #getu
#አፍሪካ_ሕብረት #ቡርኪና_ፋሶ #ኢብራሂም_ትራኦሬ #ኤቫሪስቴ_ንዳይሺሚዬ #ሳሕል #አፍሪካ #ሰላም_እና_መረጋጋት
#ethiopia | የቡሩንዲ ፕሬዝዳንት እና የወቅቱ የአፍሪካ ሕብረት ሊቀመንበር ኤቫሪስቴ ንዳይሺሚዬ በኡጋዱጉ ባደረጉት ይፋዊ የሥራ ጉብኝት፣ ከቡርኪና ፋሶው መሪ ኢብራሂም ትራኦሬ ጋር በወቅታዊና ቀጣናዊ ጉዳዮች ላይ መክረዋል። ይህ ስብሰባ በተለይ በሕብረቱ እና በታገዱት የሳሕል ቀጣና ሀገራት መካከል ያለውን ግንኙነት ለማደስ አዲስ ተስፋ የፈነጠቀ ሆኗል።
ፕሬዝዳንት ንዳይሺሚዬ፣ መሪው ኢብራሂም ትራኦሬ ለሀገራዊ ሰላምና መረጋጋት እያሳዩት ያለውን "ጽኑ ቁርጠኝነት" በማድነቅ የእንኳን ደስ አለዎት መልዕክት አስተላልፈዋል።
ሊቀመንበሩ ስለ ሳሕል ቀጣና እና ስለ ቡርኪና ፋሶ ህዝብ ነባራዊ ሁኔታ ካለባቸው የተዛባ ግንዛቤ ወጥተው፣ አሁን "ተጨባጭ እውነታውን" በተሻለ ሁኔታ መረዳታቸውን ገልጸዋል።
ወደ የጋራ መጻኢ እድል በጋራ ለመጓዝ የሚያስችል፣ ሀቀኛ እና በነባራዊ ሁኔታ ላይ የተመሠረተ ሪፖርት ለአፍሪካ ሕብረት ለማቅረብ ማቀዳቸውን ይፋ አድርገዋል።
ይህ ጉብኝት በዋናነት በአሁኑ ወቅት ከአባልነታቸው የታገዱት የሳሕል ሀገራት ከሕብረቱ ጋር ዳግም የሚገናኙበትን "የትብብር ድልድይ" ለመገንባትና ለማጠናከር ያለመ ነው። የቡሩንዲ ፕሬዝዳንት ጽሕፈት ቤት እንደገለጸው፣ ውይይቱ በቀጣናው ዘላቂ ሰላም ለማምጣት የሚደረገው ጥረት አካል ነው።
የስፑትኒክ ዘገባ እንደሚያመለክተው፣ ይህ ዲፕሎማሲያዊ እንቅስቃሴ በቡርኪና ፋሶ እና በጎረቤቶቿ ላይ የሚታየውን ጫና ለማርገብ ትልቅ ፋይዳ ሊኖረው ይችላል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን) #getutemesgen #getu
#አፍሪካ_ሕብረት #ቡርኪና_ፋሶ #ኢብራሂም_ትራኦሬ #ኤቫሪስቴ_ንዳይሺሚዬ #ሳሕል #አፍሪካ #ሰላም_እና_መረጋጋት
2 months ago
"ዴሞክራሲ ገዳይ ነው፤ አፍሪካውያን ሊረሱት ይገባል" — የቡርኪና ፋሶው መሪ ኢብራሂም ትራኦሬ
#ethiopia | የቡርኪና ፋሶው ወታደራዊ መሪ ካፒቴን ኢብራሂም ትራኦሬ፣ የምዕራባውያን የዴሞክራሲ ሥርዓት በአፍሪካ ምድር ላይ "ደም መፋሰስን" እንጂ እድገትን አላመጣም ሲሉ በፅኑ ተቃወሙ። መሪው ባደረጉት የቴሌቪዥን ቆይታ፣ የሀገሪቱ ሕዝብ ስለ ዴሞክራሲ ያለውን ሃሳብ "መዘንጋት" እንዳለበትና ሥርዓቱ ለአህጉሪቱ የማይበጅ "ባዕድ መጫወቻ" መሆኑን ገልጸዋል።
"ዴሞክራሲ ወይስ ጥፋት?"
ትራኦሬ በንግግራቸው ምዕራባውያን ዴሞክራሲን ለማስፈን ጣልቃ በገቡባቸው ሀገራት ሁሉ ውጤቱ ውድመት መሆኑን ጠቅሰዋል። ለዚህም እንደ አብነት ያነሱት ሊቢያን ነው።
"በሙአመር ጋዳፊ ዘመን ሕዝቡ ነፃ ትምህርት፣ ሕክምናና መኖሪያ ቤት ያገኝ ነበር፤ ምዕራባውያን ጣልቃ ገብተው ጋዳፊን ከገደሉ በኋላ ግን ሊቢያ በማብቂያ የሌለው ትርምስ ውስጥ ትገኛለች" ሲሉ የሥርዓቱን "ገዳይነት" አስረድተዋል።
መሪው በአፍሪካ ፖለቲከኞች ላይ ያላቸውን ዕይታም አልሸሸጉም። "እውነተኛ ፖለቲከኛ የሚባለው ውሸታም፣ አድርባይና በአፈ-ጮሌነት ሕዝብን የሚያታልል ነው" ያሉ ሲሆን፣ የፖለቲካ ፓርቲዎችም ለሀገር አንድነት እንቅፋትና "ከፋፋይ" በመሆናቸው በሀገራቸው እንዳይታገዱ ማድረጋቸውን ተከላክለዋል።
ከምዕራባውያን ኮፒ-ፔስት (Copy-paste) አሰራር ወጥቶ የራስን መንገድ መከተል እንደሚገባ የገለጹት ትራኦሬ፣ የሚከተሉትን ነጥቦች እንደ መፍትሄ አስቀምጠዋል፦
ከታች የሚነሳና በባሕላዊ መሪዎች የሚታገዝ አዲስ ሥርዓት መገንባት።
በቀን 6 ወይም 8 ሰዓት በመሥራት ብቻ ሀገርን ማሳደግ እንደማይቻልና አፍሪካውያን የሥራ ባህላቸውን መቀየር እንዳለባቸው አሳስበዋል።
ከምዕራባውያን ዕርዳታ መላቀቅና በኢኮኖሚም ሆነ በወታደራዊ መስክ ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ።
ካፒቴን ትራኦሬ በሐምሌ 2024 ምርጫ እንደሚያካሂዱ መጀመሪያ ላይ ቃል ገብተው የነበረ ቢሆንም፣ የሥልጣን ዘመናቸውን ለተጨማሪ 5 ዓመታት ማራዘማቸው ይታወሳል። ይህ የዴሞክራሲ "አይበጀንም" ንግግራቸውም በሥልጣን ላይ ለቆዩባቸው ዓመታት እንደ ርዕዮተ-ዓለማዊ መከራከሪያ እየቀረበ ይገኛል።
በአጠቃላይ የ38 ዓመቱ ወጣት መሪ መልእክት ግልጽ ነው፦ "የእኛ መንገድ አብዮታዊ ነው፤ የማንንም ፈለግ አንከተልም!"
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ibrahimtraore #burkinafaso #africapolitics #democracy #sovereignty #panafricanism #westafrica #politicalshift
#ethiopia | የቡርኪና ፋሶው ወታደራዊ መሪ ካፒቴን ኢብራሂም ትራኦሬ፣ የምዕራባውያን የዴሞክራሲ ሥርዓት በአፍሪካ ምድር ላይ "ደም መፋሰስን" እንጂ እድገትን አላመጣም ሲሉ በፅኑ ተቃወሙ። መሪው ባደረጉት የቴሌቪዥን ቆይታ፣ የሀገሪቱ ሕዝብ ስለ ዴሞክራሲ ያለውን ሃሳብ "መዘንጋት" እንዳለበትና ሥርዓቱ ለአህጉሪቱ የማይበጅ "ባዕድ መጫወቻ" መሆኑን ገልጸዋል።
"ዴሞክራሲ ወይስ ጥፋት?"
ትራኦሬ በንግግራቸው ምዕራባውያን ዴሞክራሲን ለማስፈን ጣልቃ በገቡባቸው ሀገራት ሁሉ ውጤቱ ውድመት መሆኑን ጠቅሰዋል። ለዚህም እንደ አብነት ያነሱት ሊቢያን ነው።
"በሙአመር ጋዳፊ ዘመን ሕዝቡ ነፃ ትምህርት፣ ሕክምናና መኖሪያ ቤት ያገኝ ነበር፤ ምዕራባውያን ጣልቃ ገብተው ጋዳፊን ከገደሉ በኋላ ግን ሊቢያ በማብቂያ የሌለው ትርምስ ውስጥ ትገኛለች" ሲሉ የሥርዓቱን "ገዳይነት" አስረድተዋል።
መሪው በአፍሪካ ፖለቲከኞች ላይ ያላቸውን ዕይታም አልሸሸጉም። "እውነተኛ ፖለቲከኛ የሚባለው ውሸታም፣ አድርባይና በአፈ-ጮሌነት ሕዝብን የሚያታልል ነው" ያሉ ሲሆን፣ የፖለቲካ ፓርቲዎችም ለሀገር አንድነት እንቅፋትና "ከፋፋይ" በመሆናቸው በሀገራቸው እንዳይታገዱ ማድረጋቸውን ተከላክለዋል።
ከምዕራባውያን ኮፒ-ፔስት (Copy-paste) አሰራር ወጥቶ የራስን መንገድ መከተል እንደሚገባ የገለጹት ትራኦሬ፣ የሚከተሉትን ነጥቦች እንደ መፍትሄ አስቀምጠዋል፦
ከታች የሚነሳና በባሕላዊ መሪዎች የሚታገዝ አዲስ ሥርዓት መገንባት።
በቀን 6 ወይም 8 ሰዓት በመሥራት ብቻ ሀገርን ማሳደግ እንደማይቻልና አፍሪካውያን የሥራ ባህላቸውን መቀየር እንዳለባቸው አሳስበዋል።
ከምዕራባውያን ዕርዳታ መላቀቅና በኢኮኖሚም ሆነ በወታደራዊ መስክ ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ።
ካፒቴን ትራኦሬ በሐምሌ 2024 ምርጫ እንደሚያካሂዱ መጀመሪያ ላይ ቃል ገብተው የነበረ ቢሆንም፣ የሥልጣን ዘመናቸውን ለተጨማሪ 5 ዓመታት ማራዘማቸው ይታወሳል። ይህ የዴሞክራሲ "አይበጀንም" ንግግራቸውም በሥልጣን ላይ ለቆዩባቸው ዓመታት እንደ ርዕዮተ-ዓለማዊ መከራከሪያ እየቀረበ ይገኛል።
በአጠቃላይ የ38 ዓመቱ ወጣት መሪ መልእክት ግልጽ ነው፦ "የእኛ መንገድ አብዮታዊ ነው፤ የማንንም ፈለግ አንከተልም!"
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ibrahimtraore #burkinafaso #africapolitics #democracy #sovereignty #panafricanism #westafrica #politicalshift
2 months ago
ትራኦሬ ከኤለን መስክ‼️
ኢብራሂም ትራኦሬ በቡርኪና ፋሶ ውስጥ ከኤሎን መስክ ጋር የተገናኙትን የንግድ ኩባንያዎችን በሙሉ አግዷል።
ይህ የሆነው በቴክኖሎጂ ዘርፉ በጣም ትርፋማ የሆነው እና የአለም ቁጥር አንድ ባለሃብት ኢሎን መስክ በደቡብ አፍሪካ ለስታርሊንክ ፍቃድ አለማግኘቱን ተከትሎ "ፍቃድ ያልተሰጠኝ ጥቁር ስላልሆንኩ ነው" የሚል ስድብ አዘል ንግግር በማድረጉ ነው።
የቡርኪናፋሶው መሪ ትራኦሬ እንዲህ ብሏል፣ "ፍትሃዊ ጨዋታ ነው፣የትኛውንም የአፍሪካን ሀገር እየተሳደቡ ንግድዎን በቡርኪና ፋሶ እንዲቀጥል መጠበቅ አይቻልም። ይህ አዲስ አፍሪካ ነው፣የለመድከው አፍሪካ አይደለችም።" ብለዋል።
seledadotio
seledadotio
ኢብራሂም ትራኦሬ በቡርኪና ፋሶ ውስጥ ከኤሎን መስክ ጋር የተገናኙትን የንግድ ኩባንያዎችን በሙሉ አግዷል።
ይህ የሆነው በቴክኖሎጂ ዘርፉ በጣም ትርፋማ የሆነው እና የአለም ቁጥር አንድ ባለሃብት ኢሎን መስክ በደቡብ አፍሪካ ለስታርሊንክ ፍቃድ አለማግኘቱን ተከትሎ "ፍቃድ ያልተሰጠኝ ጥቁር ስላልሆንኩ ነው" የሚል ስድብ አዘል ንግግር በማድረጉ ነው።
የቡርኪናፋሶው መሪ ትራኦሬ እንዲህ ብሏል፣ "ፍትሃዊ ጨዋታ ነው፣የትኛውንም የአፍሪካን ሀገር እየተሳደቡ ንግድዎን በቡርኪና ፋሶ እንዲቀጥል መጠበቅ አይቻልም። ይህ አዲስ አፍሪካ ነው፣የለመድከው አፍሪካ አይደለችም።" ብለዋል።
seledadotio
seledadotio
3 months ago
የሳህሉ "ነበልባል"፦ የካፒቴን ኢብራሂም ትራኦሬ አዲስ የለውጥ መንገድ
#ethiopia | በምዕራብ አፍሪካዊቷ ሀገር ቡርኪና ፋሶ፣ በወጣቱ መሪ ካፒቴን ኢብራሂም ትራኦሬ የሚመራው አዲስ የፖለቲካ እና የኢኮኖሚ ምዕራፍ በመላው አህጉሪቱ ትኩረት እየሳበ ይገኛል። እ.ኤ.አ በ2022 በመፈንቅለ መንግሥት ሥልጣን የያዙት የ36 ዓመቱ ትራኦሬ፣ ሀገራቸውን ከምዕራባውያን ጥገኝነት በማላቀቅና በራስ የመመራት መንፈስን በመቅረጽ ላይ ያተኮሩ ደፋር እርምጃዎችን እየወሰዱ ነው።
ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነትና የወርቅ ሀብት
የመሪው ዋነኛ ስኬት ተደርጎ የሚጠቀሰው የሀገሪቱን የተፈጥሮ ሀብት ለዜጎች ጥቅም ማዋል ነው። ቡርኪና ፋሶ ወርቋን በራሷ አቅም እንድታጣራ የሚያስችል ብሔራዊ ፋብሪካ በመገንባት ላይ ስትሆን፣ አዳዲስ የማዕድን ሕጎችም መንግሥት በፕሮጀክቶች ላይ ቢያንስ የ10 በመቶ ድርሻ እንዲኖረው አስገዳጅ አድርገዋል። ይህ እርምጃ ቀደም ሲል ወደ ውጭ ይፈስ የነበረውን ሀብት በሀገር ውስጥ ለማስቀረት ያለመ ነው።
አስደናቂ የኢኮኖሚ ማሻሻያዎች
በመንግሥታቸው የተወሰዱ የገንዘብና የግብርና ፖሊሲዎች ተጨባጭ ውጤት እያሳዩ መሆኑን መረጃዎች ያመለክታሉ፦
* የዋጋ ግሽበት ቁጥጥር፦ በአንድ ወቅት 14 በመቶ የነበረው የዋጋ ግሽበት ወደ 2.4 በመቶ ዝቅ እንዲል ተደርጓል።
* የኢኮኖሚ እድገት፦ ለ2024 እና 2025 በዓመት በአማካይ የ4.8 በመቶ እድገት እንደሚመዘገብ ይጠበቃል።
* የምግብ ዋስትና፦ በግብርናው ዘርፍ የሚደረገው ኢንቨስትመንት ሀገሪቱን በምግብ ራስን ወደ መቻል እያገፋት ይገኛል።
ያልተቀረፉ ፈተናዎች
ምንም እንኳን በኢኮኖሚው ረገድ ተስፋ ሰጪ ውጤቶች ቢታዩም፣ የትራኦሬ መንግሥት ከባድ የደኅንነት ስጋቶች ተጋርጠውበታል። በአክራሪ ታጣቂዎች የሚሰነዘረው ጥቃትና ተደጋጋሚ የግድያ ሙከራዎች ለሥልጣናቸው ዋነኛ ስጋት ሆነዋል። በተጨማሪም፣ የዲሞክራሲያዊ ምርጫ መራዘም በዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ዘንድ ጥያቄዎችን እያስነሳ ይገኛል።
ካፒቴን ትራኦሬ ለብዙ የአፍሪካ ወጣቶች የሉዓላዊነት ተምሳሌት ሆነው ቢታዩም፣ የጀመሩት "የውጤት እንጂ የቃል" ጉዞ ዘላቂነት ያለው ለውጥ ያመጣ እንደሆነ ጊዜ የሚፈታው ይሆናል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #መናኸሪያFM #ቡርኪናፋሶ #ኢብራሂምትራኦሬ #አፍሪካ #ኢኮኖሚ #ሉዓላዊነት #ሳህል
#ethiopia | በምዕራብ አፍሪካዊቷ ሀገር ቡርኪና ፋሶ፣ በወጣቱ መሪ ካፒቴን ኢብራሂም ትራኦሬ የሚመራው አዲስ የፖለቲካ እና የኢኮኖሚ ምዕራፍ በመላው አህጉሪቱ ትኩረት እየሳበ ይገኛል። እ.ኤ.አ በ2022 በመፈንቅለ መንግሥት ሥልጣን የያዙት የ36 ዓመቱ ትራኦሬ፣ ሀገራቸውን ከምዕራባውያን ጥገኝነት በማላቀቅና በራስ የመመራት መንፈስን በመቅረጽ ላይ ያተኮሩ ደፋር እርምጃዎችን እየወሰዱ ነው።
ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነትና የወርቅ ሀብት
የመሪው ዋነኛ ስኬት ተደርጎ የሚጠቀሰው የሀገሪቱን የተፈጥሮ ሀብት ለዜጎች ጥቅም ማዋል ነው። ቡርኪና ፋሶ ወርቋን በራሷ አቅም እንድታጣራ የሚያስችል ብሔራዊ ፋብሪካ በመገንባት ላይ ስትሆን፣ አዳዲስ የማዕድን ሕጎችም መንግሥት በፕሮጀክቶች ላይ ቢያንስ የ10 በመቶ ድርሻ እንዲኖረው አስገዳጅ አድርገዋል። ይህ እርምጃ ቀደም ሲል ወደ ውጭ ይፈስ የነበረውን ሀብት በሀገር ውስጥ ለማስቀረት ያለመ ነው።
አስደናቂ የኢኮኖሚ ማሻሻያዎች
በመንግሥታቸው የተወሰዱ የገንዘብና የግብርና ፖሊሲዎች ተጨባጭ ውጤት እያሳዩ መሆኑን መረጃዎች ያመለክታሉ፦
* የዋጋ ግሽበት ቁጥጥር፦ በአንድ ወቅት 14 በመቶ የነበረው የዋጋ ግሽበት ወደ 2.4 በመቶ ዝቅ እንዲል ተደርጓል።
* የኢኮኖሚ እድገት፦ ለ2024 እና 2025 በዓመት በአማካይ የ4.8 በመቶ እድገት እንደሚመዘገብ ይጠበቃል።
* የምግብ ዋስትና፦ በግብርናው ዘርፍ የሚደረገው ኢንቨስትመንት ሀገሪቱን በምግብ ራስን ወደ መቻል እያገፋት ይገኛል።
ያልተቀረፉ ፈተናዎች
ምንም እንኳን በኢኮኖሚው ረገድ ተስፋ ሰጪ ውጤቶች ቢታዩም፣ የትራኦሬ መንግሥት ከባድ የደኅንነት ስጋቶች ተጋርጠውበታል። በአክራሪ ታጣቂዎች የሚሰነዘረው ጥቃትና ተደጋጋሚ የግድያ ሙከራዎች ለሥልጣናቸው ዋነኛ ስጋት ሆነዋል። በተጨማሪም፣ የዲሞክራሲያዊ ምርጫ መራዘም በዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ዘንድ ጥያቄዎችን እያስነሳ ይገኛል።
ካፒቴን ትራኦሬ ለብዙ የአፍሪካ ወጣቶች የሉዓላዊነት ተምሳሌት ሆነው ቢታዩም፣ የጀመሩት "የውጤት እንጂ የቃል" ጉዞ ዘላቂነት ያለው ለውጥ ያመጣ እንደሆነ ጊዜ የሚፈታው ይሆናል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #መናኸሪያFM #ቡርኪናፋሶ #ኢብራሂምትራኦሬ #አፍሪካ #ኢኮኖሚ #ሉዓላዊነት #ሳህል
Sponsored by
Surafel
5 months ago
በቡርኪና ፋሶ በፕሬዝዳንት ኢብራሂም ትራኦሬ ላይ የታቀደ የግድያ ሴራ መክሸፉ ተነገረ
የቡርኪና ፋሶ የደህንነት ሚኒስትር ማሃማዱ ሳና እንደገለጹት፣ ሴራው የተቀነባበረው እ.ኤ.አ. በ2022 በካፒቴን ትራኦሬ አማካኝነት ከስልጣን በተወገዱት የቀድሞው የአገሪቱ መሪ ሌተናል ኮሎኔል ፖል ሄንሪ ዳሚባ ነው።
እንደ ሚኒስትሩ ገለጻ፣ ይህ ሀገሪቱን የማናጋት እና ፕሬዝዳንቱን የመግደል እቅድ የገንዘብ ድጋፍ የተደረገለት ከጎረቤት ሀገር ኮትዲቩዋር (Ivory Coast) ነው። ይሁን እንጂ እስካሁን ድረስ ከኮትዲቩዋር መንግስትም ሆነ ከሌተናል ኮሎኔል ዳሚባ የተሰጠ ምንም ዓይነት ምላሽ የለም።
ካፒቴን ኢብራሂም ትራኦሬ ስልጣን ከያዙ በኋላ በተደጋጋሚ የመፈንቅለ መንግስት ሙከራዎች እንደተደረጉባቸው የሚታወቅ ሲሆን፣ የቡርኪና ፋሶ መንግስት ለእነዚህ ሙከራዎች ኮትዲቩዋርን ተባባሪ ናት በማለት በተደጋጋሚ ሲከስ ቆይቷል።
seledadotio.
seledadotio
የቡርኪና ፋሶ የደህንነት ሚኒስትር ማሃማዱ ሳና እንደገለጹት፣ ሴራው የተቀነባበረው እ.ኤ.አ. በ2022 በካፒቴን ትራኦሬ አማካኝነት ከስልጣን በተወገዱት የቀድሞው የአገሪቱ መሪ ሌተናል ኮሎኔል ፖል ሄንሪ ዳሚባ ነው።
እንደ ሚኒስትሩ ገለጻ፣ ይህ ሀገሪቱን የማናጋት እና ፕሬዝዳንቱን የመግደል እቅድ የገንዘብ ድጋፍ የተደረገለት ከጎረቤት ሀገር ኮትዲቩዋር (Ivory Coast) ነው። ይሁን እንጂ እስካሁን ድረስ ከኮትዲቩዋር መንግስትም ሆነ ከሌተናል ኮሎኔል ዳሚባ የተሰጠ ምንም ዓይነት ምላሽ የለም።
ካፒቴን ኢብራሂም ትራኦሬ ስልጣን ከያዙ በኋላ በተደጋጋሚ የመፈንቅለ መንግስት ሙከራዎች እንደተደረጉባቸው የሚታወቅ ሲሆን፣ የቡርኪና ፋሶ መንግስት ለእነዚህ ሙከራዎች ኮትዲቩዋርን ተባባሪ ናት በማለት በተደጋጋሚ ሲከስ ቆይቷል።
seledadotio.
seledadotio
5 months ago
በቡርኪና ፋሶ በፕሬዝዳንት ኢብራሂም ትራኦሬ ላይ የታቀደ የግድያ ሴራ መክሸፉ ተነገረ
የቡርኪና ፋሶ የደህንነት ሚኒስትር ማሃማዱ ሳና እንደገለጹት፣ ሴራው የተቀነባበረው እ.ኤ.አ. በ2022 በካፒቴን ትራኦሬ አማካኝነት ከስልጣን በተወገዱት የቀድሞው የአገሪቱ መሪ ሌተናል ኮሎኔል ፖል ሄንሪ ዳሚባ ነው።
እንደ ሚኒስትሩ ገለጻ፣ ይህ ሀገሪቱን የማናጋት እና ፕሬዝዳንቱን የመግደል እቅድ የገንዘብ ድጋፍ የተደረገለት ከጎረቤት ሀገር ኮትዲቩዋር (Ivory Coast) ነው። ይሁን እንጂ እስካሁን ድረስ ከኮትዲቩዋር መንግስትም ሆነ ከሌተናል ኮሎኔል ዳሚባ የተሰጠ ምንም ዓይነት ምላሽ የለም።
ካፒቴን ኢብራሂም ትራኦሬ ስልጣን ከያዙ በኋላ በተደጋጋሚ የመፈንቅለ መንግስት ሙከራዎች እንደተደረጉባቸው የሚታወቅ ሲሆን፣ የቡርኪና ፋሶ መንግስት ለእነዚህ ሙከራዎች ኮትዲቩዋርን ተባባሪ ናት በማለት በተደጋጋሚ ሲከስ ቆይቷል።
የቡርኪና ፋሶ የደህንነት ሚኒስትር ማሃማዱ ሳና እንደገለጹት፣ ሴራው የተቀነባበረው እ.ኤ.አ. በ2022 በካፒቴን ትራኦሬ አማካኝነት ከስልጣን በተወገዱት የቀድሞው የአገሪቱ መሪ ሌተናል ኮሎኔል ፖል ሄንሪ ዳሚባ ነው።
እንደ ሚኒስትሩ ገለጻ፣ ይህ ሀገሪቱን የማናጋት እና ፕሬዝዳንቱን የመግደል እቅድ የገንዘብ ድጋፍ የተደረገለት ከጎረቤት ሀገር ኮትዲቩዋር (Ivory Coast) ነው። ይሁን እንጂ እስካሁን ድረስ ከኮትዲቩዋር መንግስትም ሆነ ከሌተናል ኮሎኔል ዳሚባ የተሰጠ ምንም ዓይነት ምላሽ የለም።
ካፒቴን ኢብራሂም ትራኦሬ ስልጣን ከያዙ በኋላ በተደጋጋሚ የመፈንቅለ መንግስት ሙከራዎች እንደተደረጉባቸው የሚታወቅ ሲሆን፣ የቡርኪና ፋሶ መንግስት ለእነዚህ ሙከራዎች ኮትዲቩዋርን ተባባሪ ናት በማለት በተደጋጋሚ ሲከስ ቆይቷል።
6 months ago
ትራኦሬ ዊግ ከለከሉ‼️
የቡርኪናፋሶው መሪ ካፒቴን ኢብራሂም ትራኦሬ ከውጪ ወደ ሀገር ውስጥ የሚገቡ አርቲፊሻል ጸጉር (በተለምዶ ዊግ በመባል የሚታወቁት) ወደ አገራቸው ቡርኪና-ፋሶ እንዳይገቡ ከልክለዋል። አፍሪካ አህጉር እንጂ "ሙዚየም አይደለችም" ብለዋል።
seledadotio
seledadotio
የቡርኪናፋሶው መሪ ካፒቴን ኢብራሂም ትራኦሬ ከውጪ ወደ ሀገር ውስጥ የሚገቡ አርቲፊሻል ጸጉር (በተለምዶ ዊግ በመባል የሚታወቁት) ወደ አገራቸው ቡርኪና-ፋሶ እንዳይገቡ ከልክለዋል። አፍሪካ አህጉር እንጂ "ሙዚየም አይደለችም" ብለዋል።
seledadotio
seledadotio
6 months ago
ኢብራሂም ትራኦሬ "ጥሩ መሪ አይደለም"!/ሙሳሊያ ሙዳቫዲ/
የኬንያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ኢብራሂም
ትራኦሬ "ጥሩ መሪ አይደለም" ሲሉ መናገራቸው ተሰማ ።
የኬንያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሙሳሊያ ሙዳቫዲ ስለ ቡርኪናፋሶ መሪ ኢብራሂም ትራኦሬ ጠንከር ያለ አስተያየት ከሰጡ በኋላ ክርክር አስነስተዋል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ የቡርኪናፋሶው ኢብራሂም ትራኦሬ ጥሩ መሪ አይደለም ሲሉ ትችት ሰንዝረዋል፡፡
የኬንያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሙሳሊያ ሙዳቫዲ፣ ስለ ቡርኪናፋሶ መሪ ኢብራሂም ትራኦሬ የሰነዘሩት "እውነተኛ መሪ ሽጉጥ በወገቡ ላይ መያዝ ወይም መሳሪያ በጠረጴዛው ላይ ማሳየት አያስፈልገውም ብለዋል። እንደ እርሳቸው ገለጻ፣ አመራር በተቋማት፣ በዲሞክራሲ እና በተጠያቂነት ላይ መገንባት አለበት - በኃይል አይደለም።ብለዋል ።
የሙዳቫዲ ንግግራቸው የመጣው በምዕራብ አፍሪካ የሚገኙ ወታደራዊ መሪዎች በተለይም በወጣቶች ዘንድ በጠንካራ ፀረ-ኢምፔሪያሊዝም አቋማቸው እና በደህንነት ቃል ኪዳናቸው ምክንያት ተወዳጅነትን እያገኙ ባሉበት ወቅት ሲሆን ይህም እያስተቻቸዉ ይገኛል ።
የኬንያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ኢብራሂም
ትራኦሬ "ጥሩ መሪ አይደለም" ሲሉ መናገራቸው ተሰማ ።
የኬንያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሙሳሊያ ሙዳቫዲ ስለ ቡርኪናፋሶ መሪ ኢብራሂም ትራኦሬ ጠንከር ያለ አስተያየት ከሰጡ በኋላ ክርክር አስነስተዋል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ የቡርኪናፋሶው ኢብራሂም ትራኦሬ ጥሩ መሪ አይደለም ሲሉ ትችት ሰንዝረዋል፡፡
የኬንያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሙሳሊያ ሙዳቫዲ፣ ስለ ቡርኪናፋሶ መሪ ኢብራሂም ትራኦሬ የሰነዘሩት "እውነተኛ መሪ ሽጉጥ በወገቡ ላይ መያዝ ወይም መሳሪያ በጠረጴዛው ላይ ማሳየት አያስፈልገውም ብለዋል። እንደ እርሳቸው ገለጻ፣ አመራር በተቋማት፣ በዲሞክራሲ እና በተጠያቂነት ላይ መገንባት አለበት - በኃይል አይደለም።ብለዋል ።
የሙዳቫዲ ንግግራቸው የመጣው በምዕራብ አፍሪካ የሚገኙ ወታደራዊ መሪዎች በተለይም በወጣቶች ዘንድ በጠንካራ ፀረ-ኢምፔሪያሊዝም አቋማቸው እና በደህንነት ቃል ኪዳናቸው ምክንያት ተወዳጅነትን እያገኙ ባሉበት ወቅት ሲሆን ይህም እያስተቻቸዉ ይገኛል ።
Sponsored by
Surafel
7 months ago
ቡርኪናፋሶ የምርጫ ኮሚሽኗን አፍርሳለች
#ethiopia | የቡርኪናፋሶ የሽግግር ጉባኤ ላለፉት 20 አመታት የነበረው ገለልተኛ የምርጫ ኮሚሽን እንዲፈርስ ወስኗል።
የቡርኪናፋሶ ወታደራዊ አገዛዝ የምርጫ ኮሚሽኑን ገንዘብ ማጥፊያ እና የውጪ ተጽዕኖ ያለበት ሲል ገልፆታል።
በአዲሱ ህግ መሰረትም የግዛት አስተዳር ሚኒስትር ምርጫ የማደራጀት ኃላፊነት በኮሚሽኑ ምትክ ተሰጥቶታል።
በመፈንቅለ መንግስት በ2022 ስልጣን የያዘው የኢብራሂም ትራኦሬ አገዛዝ በ21 ወራት ውስጥ ሲቪል መንግስት ይመሰረታል ብሎ የነበረ ቢሆንም የሽግግር ጊዜውን በ5 ዓመት በማራዘም ትሪኦሬም በመጪው ምርጫ እንዲወዳደሩ ፈቅዷል።
አፍሪካ ኒውስ
#ethiopia | የቡርኪናፋሶ የሽግግር ጉባኤ ላለፉት 20 አመታት የነበረው ገለልተኛ የምርጫ ኮሚሽን እንዲፈርስ ወስኗል።
የቡርኪናፋሶ ወታደራዊ አገዛዝ የምርጫ ኮሚሽኑን ገንዘብ ማጥፊያ እና የውጪ ተጽዕኖ ያለበት ሲል ገልፆታል።
በአዲሱ ህግ መሰረትም የግዛት አስተዳር ሚኒስትር ምርጫ የማደራጀት ኃላፊነት በኮሚሽኑ ምትክ ተሰጥቶታል።
በመፈንቅለ መንግስት በ2022 ስልጣን የያዘው የኢብራሂም ትራኦሬ አገዛዝ በ21 ወራት ውስጥ ሲቪል መንግስት ይመሰረታል ብሎ የነበረ ቢሆንም የሽግግር ጊዜውን በ5 ዓመት በማራዘም ትሪኦሬም በመጪው ምርጫ እንዲወዳደሩ ፈቅዷል።
አፍሪካ ኒውስ
9 months ago
ቡርኪና ፋሶ ለሁሉም የአፍሪካ ተጓዦች ከቪዛ ነፃ ጉዞን ፈቀደች
#ethiopia | ቡርኪና ፋሶ ለሁሉም የአፍሪካ ተጓዦች ከቪዛ ነፃ ወደ ሃገሪቷ መግባት የሚያስችል ፖሊሲን አስተዋውቃለች፡፡
ሰዎች እና ሸቀጦች ወደ ሀገሪቱ የሚገቡበትን ሁኔታ ይበልጥ ምቹ ለማድረግ እና ቃጣናዊ ትስስርን ለማጠናከር በማለም የተወሰነው ይህ ውሳኔ፤ ተጓዦች ጉዟቸውን ለማፀደቅ በበይነ መረብ በማመልከት ያለ ምንም የቪዛ ክፍያ ወደ ሃገሪቱ ለመግባት የሚያስችላቸው ይሆናል፡፡
በዚህም ሃገሪቱ ለአፍሪካ ሃገራት የጉዞ መስፈርቶችን ካቀለሉ ከነ ጋና፣ ሩዋንዳ እና ኬንያ ጋር እንድትሰለፍ አስችሏታል፡፡
ውሳኔው ከፈረንጆቹ 2022 ጀምሮ ስልጣን ላይ ያሉትን የሃገሪቱ ወታደራዊ መሪ ኢብራሂም ትራኦሬን የፓን አፍሪካኒዝም ሃሳብ የሚያንፀባርቅ መሆኑን ቢቢሲ ዘግቧል፡፡
ይህ ውሳኔ የሃገሪቱን የቱሪዝም ዘርፍ ለማሳደግ እና ባህሏንም በማስተዋወቅ ዓለም አቀፍ ትኩረትንም እንድትስብ ያደርጋል ተብሎ ታምኗል፡፡
ሆኖም የሃገሪቱ ውሳኔ ከጎረቤት ሃገሮቿ ጋር ያላትን ግንኙነት ስለማጠናከሩ እርግጠኛ መሆን እንደማይቻልም ዘገባው አመላክቷል፡፡
ቡርኪና ፋሶ፣ ማሊ እና ኒጀር ሌላ ህብረት ለመፍጠር የምዕራብ አፍሪካ መንግስታት የኢኮኖሚ ማህበረሰብ (ኢኮዋስ) ለቀው መውጣታቸውን ዘገባው አስታውሷል፡፡
AMN
#ethiopia | ቡርኪና ፋሶ ለሁሉም የአፍሪካ ተጓዦች ከቪዛ ነፃ ወደ ሃገሪቷ መግባት የሚያስችል ፖሊሲን አስተዋውቃለች፡፡
ሰዎች እና ሸቀጦች ወደ ሀገሪቱ የሚገቡበትን ሁኔታ ይበልጥ ምቹ ለማድረግ እና ቃጣናዊ ትስስርን ለማጠናከር በማለም የተወሰነው ይህ ውሳኔ፤ ተጓዦች ጉዟቸውን ለማፀደቅ በበይነ መረብ በማመልከት ያለ ምንም የቪዛ ክፍያ ወደ ሃገሪቱ ለመግባት የሚያስችላቸው ይሆናል፡፡
በዚህም ሃገሪቱ ለአፍሪካ ሃገራት የጉዞ መስፈርቶችን ካቀለሉ ከነ ጋና፣ ሩዋንዳ እና ኬንያ ጋር እንድትሰለፍ አስችሏታል፡፡
ውሳኔው ከፈረንጆቹ 2022 ጀምሮ ስልጣን ላይ ያሉትን የሃገሪቱ ወታደራዊ መሪ ኢብራሂም ትራኦሬን የፓን አፍሪካኒዝም ሃሳብ የሚያንፀባርቅ መሆኑን ቢቢሲ ዘግቧል፡፡
ይህ ውሳኔ የሃገሪቱን የቱሪዝም ዘርፍ ለማሳደግ እና ባህሏንም በማስተዋወቅ ዓለም አቀፍ ትኩረትንም እንድትስብ ያደርጋል ተብሎ ታምኗል፡፡
ሆኖም የሃገሪቱ ውሳኔ ከጎረቤት ሃገሮቿ ጋር ያላትን ግንኙነት ስለማጠናከሩ እርግጠኛ መሆን እንደማይቻልም ዘገባው አመላክቷል፡፡
ቡርኪና ፋሶ፣ ማሊ እና ኒጀር ሌላ ህብረት ለመፍጠር የምዕራብ አፍሪካ መንግስታት የኢኮኖሚ ማህበረሰብ (ኢኮዋስ) ለቀው መውጣታቸውን ዘገባው አስታውሷል፡፡
AMN
9 months ago
ቡርኪናፋሶ ለአፍሪካውያን ተጓዦች የቪዛ ክፍያን ሰረዘች
ቡርኪናፋሶ ሰዎችን እና ሸቀጦችን ወደ ሀገሪቱ በቀላሉ የሚገቡበትን ሁኔታ ለማመቻቸት ለሁሉም አፍሪካውያን ተጓዦች ከቪዛ ነጻ የሆነ መግቢያ አስተዋውቋል።
በወታደራዊ መሪ ካፒቴን ኢብራሂም ትራኦሬ የተመራውን የካቢኔ ስብሰባ ተከትሎ የሀገሪቱ የደህንነት ሚኒስትር ማሃማዱ ሳና "ከአሁን ጀምሮ ማንኛውም የአፍሪካ ሀገር ወደ ቡርኪናፋሶ ለመጓዝ የሚፈልግ ዜጋ ምንም አይነት ክፍያ አይከፍልም" ብለዋል።
አፍሪካውያን ጎብኝዎች ግን የኦንላይን ቪዛ ማመልከቻ እንዲያቀርቡ ይጠበቅባቸዋል፣ ከመፅደቁ በፊት ግን ይገመገማል ሲሉ ሚኒስትሩ አብራርተዋል።
የምዕራብ አፍሪካ ሀገር እንደ ጋና፣ ሩዋንዳ እና ኬንያ ለአፍሪካ ጎብኚዎች የጉዞ መስፈርቶችን ያቃለሉ ሀገራትን ተቀላቅላለች።
seledadotio
seledadotio
ቡርኪናፋሶ ሰዎችን እና ሸቀጦችን ወደ ሀገሪቱ በቀላሉ የሚገቡበትን ሁኔታ ለማመቻቸት ለሁሉም አፍሪካውያን ተጓዦች ከቪዛ ነጻ የሆነ መግቢያ አስተዋውቋል።
በወታደራዊ መሪ ካፒቴን ኢብራሂም ትራኦሬ የተመራውን የካቢኔ ስብሰባ ተከትሎ የሀገሪቱ የደህንነት ሚኒስትር ማሃማዱ ሳና "ከአሁን ጀምሮ ማንኛውም የአፍሪካ ሀገር ወደ ቡርኪናፋሶ ለመጓዝ የሚፈልግ ዜጋ ምንም አይነት ክፍያ አይከፍልም" ብለዋል።
አፍሪካውያን ጎብኝዎች ግን የኦንላይን ቪዛ ማመልከቻ እንዲያቀርቡ ይጠበቅባቸዋል፣ ከመፅደቁ በፊት ግን ይገመገማል ሲሉ ሚኒስትሩ አብራርተዋል።
የምዕራብ አፍሪካ ሀገር እንደ ጋና፣ ሩዋንዳ እና ኬንያ ለአፍሪካ ጎብኚዎች የጉዞ መስፈርቶችን ያቃለሉ ሀገራትን ተቀላቅላለች።
seledadotio
seledadotio
9 months ago
ቡርኪናፋሶ ለአፍሪካውያን ተጓዦች የቪዛ ክፍያን ሰረዘች
ቡርኪናፋሶ ሰዎችን እና ሸቀጦችን ወደ ሀገሪቱ በቀላሉ የሚገቡበትን ሁኔታ ለማመቻቸት ለሁሉም አፍሪካውያን ተጓዦች ከቪዛ ነጻ የሆነ መግቢያ አስተዋውቋል።
በወታደራዊ መሪ ካፒቴን ኢብራሂም ትራኦሬ የተመራውን የካቢኔ ስብሰባ ተከትሎ የሀገሪቱ የደህንነት ሚኒስትር ማሃማዱ ሳና "ከአሁን ጀምሮ ማንኛውም የአፍሪካ ሀገር ወደ ቡርኪናፋሶ ለመጓዝ የሚፈልግ ዜጋ ምንም አይነት ክፍያ አይከፍልም" ብለዋል።
አፍሪካውያን ጎብኝዎች ግን የኦንላይን ቪዛ ማመልከቻ እንዲያቀርቡ ይጠበቅባቸዋል፣ ከመፅደቁ በፊት ግን ይገመገማል ሲሉ ሚኒስትሩ አብራርተዋል።
የምዕራብ አፍሪካ ሀገር እንደ ጋና፣ ሩዋንዳ እና ኬንያ ለአፍሪካ ጎብኚዎች የጉዞ መስፈርቶችን ያቃለሉ ሀገራትን ተቀላቅላለች እንደ ቢቢሲ ዘገባ።
Ethio fm
ቡርኪናፋሶ ሰዎችን እና ሸቀጦችን ወደ ሀገሪቱ በቀላሉ የሚገቡበትን ሁኔታ ለማመቻቸት ለሁሉም አፍሪካውያን ተጓዦች ከቪዛ ነጻ የሆነ መግቢያ አስተዋውቋል።
በወታደራዊ መሪ ካፒቴን ኢብራሂም ትራኦሬ የተመራውን የካቢኔ ስብሰባ ተከትሎ የሀገሪቱ የደህንነት ሚኒስትር ማሃማዱ ሳና "ከአሁን ጀምሮ ማንኛውም የአፍሪካ ሀገር ወደ ቡርኪናፋሶ ለመጓዝ የሚፈልግ ዜጋ ምንም አይነት ክፍያ አይከፍልም" ብለዋል።
አፍሪካውያን ጎብኝዎች ግን የኦንላይን ቪዛ ማመልከቻ እንዲያቀርቡ ይጠበቅባቸዋል፣ ከመፅደቁ በፊት ግን ይገመገማል ሲሉ ሚኒስትሩ አብራርተዋል።
የምዕራብ አፍሪካ ሀገር እንደ ጋና፣ ሩዋንዳ እና ኬንያ ለአፍሪካ ጎብኚዎች የጉዞ መስፈርቶችን ያቃለሉ ሀገራትን ተቀላቅላለች እንደ ቢቢሲ ዘገባ።
Ethio fm
Sponsored by
Surafel
9 months ago
ቡርኪናፋሶ የተመሳሳይ ጾታ ግኑኝነት የሚከለክል ህግ አፀደቀች !
በካፒቴን ኢብራሂም ትራኦሬ የሚመራው የቡርኪና ፋሶ የሽግግር ፓርላማ፤ ካቢኔ የተመሳሳይ ጾታ ጋብቻም ሆነ ግኑኝነት የሚከለክል ህግ ማፅደቁ ተነገረ ።
ከአንድ ዓመት ገደማ በፊት የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነትን ወንጀል በሚያደርግ መልኩ የሀገሪቱን ቤተሰብ ህግ ለማሻሻል ያሳለፈውን ውሳኔ በመከተል ይህንን ድርጊት የሚከለክል አዋጅ ያፀደቀው ፓርላማው ድርጊቱን ገላጭ የሆኑ ባንዴራ ቀለማት ተግባራትም መፈፀም ዘብጥያ እንደሚያስወርዱ ገልጿል ።
ሰኞ ዕለት በሙሉ ድምጽ የጸደቀው አዲሱ አዋጅ የተመሳሳይ ጾታን ግንኙነት ውስጥ የተገኙ ሰዎችን እስከ አምስት ዓመት በሚደርስ እስራት እንደሚቀጡ በሀገሪቱ ዜግነት የሌላቸው አጥፊዎች ከአገር እንደሚባረሩ። ደንግጓል።
በ1960 ከፈረንሳይ ቅኝ ግዛት ነጻነቷን ያገኘቸው
ከሳህል ሀገራት አንዷ የሆነችው ቡርኪና ፋሶ ከዚህ ቀደም የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነትን ከፈቀዱ 22 የአፍሪካ ሀገራት አንዷ የነበረች ሲሆን ከዚህ በኋላ ግን ከማህበረሰቡ የሚያስገልል በገዘብና በእስር የሚስቀጣ የቤተሰብ ህግ በማድረግ በአንድ ድምፅ አጽድቋል ።
አዲሱ ህግ ወዲያውኑ ተግባራዊ ይሆናል ፣በተመሳሳይ ጾታ ግንኙነት ውስጥ ያሉ ግለሰቦች የእስር ቅጣት እና የገንዘብ ቅጣት አደጋ ላይ ናቸው ሲሉ የፍትህ ሚኒስትር ኢዳሶ ሮድሪግ ባያላ በመንግስት ቴሌቪዥን ተናግረዋል ።
ህጉ ተግባራዊ እንዲሆን የሚጠበቀው ቀጣይ ሂደት የሀገሪቱ ወታደራዊ መሪ ካፒቴን ኢብራሂም ትራኦሬ ፊርማ እንደሆነ ፋሶ 24 የዜና ወኪል ዘግቧል።
ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በርካታ በቀኝ ግዛት የተገዙ ሀገራት ፀረ ተመሳሳይ ጾታ ግንኙነት አቋም እያሳዩ የሚገኝ ሲሆን የቡርኪና ፋሶ አጋር የሆነችው ማሊም ባሳለፍነው ህዳር ወር የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነትን ወንጀል የሚያደርግ ህግ ያፀደቀች ሲሆን ጋና እና ኡጋንዳና ናይጄሪያ ይጠቀሳሉ ።
ይህን ተከትሎ መግለጫ ያወጣው የመብት ተሟጋች ድርጅት አምነስቲ ኢንተርናሽናል ማክሰኞ እንዳስታወቀው የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነት ወንጀል መደረጉ የእኩልነት መብትን የሚጥስ “አስደንጋጭ ውድቀት ነው” ብሏል። የጁንታ ዋና አዛዥ ካፒቴን ኢብራሂም ትራኦሬ ውሳኔውን እንዲቀለብስ አሳስበዋል።
የሀገሪቱ ፍትህ ሚኒስትር በበኩላቸው ይህ ዉሳኔ የቤተሰብ የማህበረሰብ ደህንነት በዜግነት እና ሀገርን ክብር የሚያስጠብቅ በመሆኑ ተፈፃሚ ይሆናል ብለዋል ሲሉ ያስነበቡት AP, AFP, Reuters, dpa, KNA የዜና ወኪሎች ናቸው ።
የኔታ ቲዩብ ዘጋቢ ፦ ታዴ የማመይ ልጅ
በካፒቴን ኢብራሂም ትራኦሬ የሚመራው የቡርኪና ፋሶ የሽግግር ፓርላማ፤ ካቢኔ የተመሳሳይ ጾታ ጋብቻም ሆነ ግኑኝነት የሚከለክል ህግ ማፅደቁ ተነገረ ።
ከአንድ ዓመት ገደማ በፊት የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነትን ወንጀል በሚያደርግ መልኩ የሀገሪቱን ቤተሰብ ህግ ለማሻሻል ያሳለፈውን ውሳኔ በመከተል ይህንን ድርጊት የሚከለክል አዋጅ ያፀደቀው ፓርላማው ድርጊቱን ገላጭ የሆኑ ባንዴራ ቀለማት ተግባራትም መፈፀም ዘብጥያ እንደሚያስወርዱ ገልጿል ።
ሰኞ ዕለት በሙሉ ድምጽ የጸደቀው አዲሱ አዋጅ የተመሳሳይ ጾታን ግንኙነት ውስጥ የተገኙ ሰዎችን እስከ አምስት ዓመት በሚደርስ እስራት እንደሚቀጡ በሀገሪቱ ዜግነት የሌላቸው አጥፊዎች ከአገር እንደሚባረሩ። ደንግጓል።
በ1960 ከፈረንሳይ ቅኝ ግዛት ነጻነቷን ያገኘቸው
ከሳህል ሀገራት አንዷ የሆነችው ቡርኪና ፋሶ ከዚህ ቀደም የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነትን ከፈቀዱ 22 የአፍሪካ ሀገራት አንዷ የነበረች ሲሆን ከዚህ በኋላ ግን ከማህበረሰቡ የሚያስገልል በገዘብና በእስር የሚስቀጣ የቤተሰብ ህግ በማድረግ በአንድ ድምፅ አጽድቋል ።
አዲሱ ህግ ወዲያውኑ ተግባራዊ ይሆናል ፣በተመሳሳይ ጾታ ግንኙነት ውስጥ ያሉ ግለሰቦች የእስር ቅጣት እና የገንዘብ ቅጣት አደጋ ላይ ናቸው ሲሉ የፍትህ ሚኒስትር ኢዳሶ ሮድሪግ ባያላ በመንግስት ቴሌቪዥን ተናግረዋል ።
ህጉ ተግባራዊ እንዲሆን የሚጠበቀው ቀጣይ ሂደት የሀገሪቱ ወታደራዊ መሪ ካፒቴን ኢብራሂም ትራኦሬ ፊርማ እንደሆነ ፋሶ 24 የዜና ወኪል ዘግቧል።
ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በርካታ በቀኝ ግዛት የተገዙ ሀገራት ፀረ ተመሳሳይ ጾታ ግንኙነት አቋም እያሳዩ የሚገኝ ሲሆን የቡርኪና ፋሶ አጋር የሆነችው ማሊም ባሳለፍነው ህዳር ወር የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነትን ወንጀል የሚያደርግ ህግ ያፀደቀች ሲሆን ጋና እና ኡጋንዳና ናይጄሪያ ይጠቀሳሉ ።
ይህን ተከትሎ መግለጫ ያወጣው የመብት ተሟጋች ድርጅት አምነስቲ ኢንተርናሽናል ማክሰኞ እንዳስታወቀው የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነት ወንጀል መደረጉ የእኩልነት መብትን የሚጥስ “አስደንጋጭ ውድቀት ነው” ብሏል። የጁንታ ዋና አዛዥ ካፒቴን ኢብራሂም ትራኦሬ ውሳኔውን እንዲቀለብስ አሳስበዋል።
የሀገሪቱ ፍትህ ሚኒስትር በበኩላቸው ይህ ዉሳኔ የቤተሰብ የማህበረሰብ ደህንነት በዜግነት እና ሀገርን ክብር የሚያስጠብቅ በመሆኑ ተፈፃሚ ይሆናል ብለዋል ሲሉ ያስነበቡት AP, AFP, Reuters, dpa, KNA የዜና ወኪሎች ናቸው ።
የኔታ ቲዩብ ዘጋቢ ፦ ታዴ የማመይ ልጅ
9 months ago
🇧🇫 ቡርኪናፋሶ : ከነፃነት ተምሳሌቷ ኢትዮጵያ ጋር የጀመርነው ወዳጅነት ይቀጥላል
* ኢትዮጵያዊው ባለሀብትና ስራ ፈጣሪ ቡርኪናፋሶ ተገኘ !
#ethiopia | በተደጋጋሚ ወደ ቡርኪናፋሶ በማምራት ኢብራሂም ትራኦሬ መንግስት ጋር ባደረገዉ ስምምነት የተለያዩ ኢትዮጵያ ሰራሽ ምርቶችን ለቡርኪናፋሶው ኤክስፖርት በማድረግ ላይ የሚገኘዉና የሀገራችንን በማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ እድገት እያስተዋወቀ ያዉወ ኢንዱስትሪያሊስት ኢንጂነር ቢጃይ ናይከር ለንግድ ልዉዉጥና ለአዳዲስ ስምምነቶች ቡርኪናፋሶ መግባቱን ከዉስጥ አዋቂዎች ሰምተናል ።
ከ126ሺ በላይ የልማት ባንክ ተበዳሪ ወጣቶችን በማሰልጠን ወደ ስራ እንዲገቡ ያስቻለው በክረምት ኮርስ 3d design machine assembly እና ai programming ከ8-12 ክፍል 100 ተማሪዎች ሙሉ ወጪያቸዉ ተሸፍኖ ያሰለጠነዉ
ከኢትዮዽያ ዉጪ ማሽኖቹን እያመረተ export እያደረገ ያለው ለብዙዎች የስራ እድል በር የከፈተው ወጣቱ ባለሀብት ወደ ቡርኪናፋሶ በማምራት በዉይይት ላይ እንደሚገኙ ተሰምቷል ።
በዉይይቱ ቤጃሺዮ ኢንዱስትሪ እና የምህንድስና ተቀም
በኢንጂነሪንግ እና በኢንዱስትሪ ልማት ዘርፎች ለቡርኪናፋሶው ወጣቶች የቴክኒክና ሙያ ሥልጠናዎች አዳዲስ መንገዶችን ስልጠና ይሰጣል - ተብሏል።
ኢትዮጵያ ማሽኖችን በማምረት የጀመረችውን ጉዞ አድናቆታቸውን የገለፁት ሚኒስተሩ "ከታላቋ ነፃ ሀገር ኢትዮጵያ ጋር ያለን ግኑኝነት ይበልጥ ያድጋል ሲሉ ተሰምተዋል ።
"ለኢንዱስትሪ እና ግብርና አስፈላጊ የሆኑ መሳሪያዎችን ለማምረት በቦታው ለማምረት ችሎታችንን ለማካፈል ፈቃደኞች ነን." ያሉት ደግሞ Bajii Nuyker ናቸዉ
ታዴ የማመይ ልጅ
* ኢትዮጵያዊው ባለሀብትና ስራ ፈጣሪ ቡርኪናፋሶ ተገኘ !
#ethiopia | በተደጋጋሚ ወደ ቡርኪናፋሶ በማምራት ኢብራሂም ትራኦሬ መንግስት ጋር ባደረገዉ ስምምነት የተለያዩ ኢትዮጵያ ሰራሽ ምርቶችን ለቡርኪናፋሶው ኤክስፖርት በማድረግ ላይ የሚገኘዉና የሀገራችንን በማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ እድገት እያስተዋወቀ ያዉወ ኢንዱስትሪያሊስት ኢንጂነር ቢጃይ ናይከር ለንግድ ልዉዉጥና ለአዳዲስ ስምምነቶች ቡርኪናፋሶ መግባቱን ከዉስጥ አዋቂዎች ሰምተናል ።
ከ126ሺ በላይ የልማት ባንክ ተበዳሪ ወጣቶችን በማሰልጠን ወደ ስራ እንዲገቡ ያስቻለው በክረምት ኮርስ 3d design machine assembly እና ai programming ከ8-12 ክፍል 100 ተማሪዎች ሙሉ ወጪያቸዉ ተሸፍኖ ያሰለጠነዉ
ከኢትዮዽያ ዉጪ ማሽኖቹን እያመረተ export እያደረገ ያለው ለብዙዎች የስራ እድል በር የከፈተው ወጣቱ ባለሀብት ወደ ቡርኪናፋሶ በማምራት በዉይይት ላይ እንደሚገኙ ተሰምቷል ።
በዉይይቱ ቤጃሺዮ ኢንዱስትሪ እና የምህንድስና ተቀም
በኢንጂነሪንግ እና በኢንዱስትሪ ልማት ዘርፎች ለቡርኪናፋሶው ወጣቶች የቴክኒክና ሙያ ሥልጠናዎች አዳዲስ መንገዶችን ስልጠና ይሰጣል - ተብሏል።
ኢትዮጵያ ማሽኖችን በማምረት የጀመረችውን ጉዞ አድናቆታቸውን የገለፁት ሚኒስተሩ "ከታላቋ ነፃ ሀገር ኢትዮጵያ ጋር ያለን ግኑኝነት ይበልጥ ያድጋል ሲሉ ተሰምተዋል ።
"ለኢንዱስትሪ እና ግብርና አስፈላጊ የሆኑ መሳሪያዎችን ለማምረት በቦታው ለማምረት ችሎታችንን ለማካፈል ፈቃደኞች ነን." ያሉት ደግሞ Bajii Nuyker ናቸዉ
ታዴ የማመይ ልጅ
9 months ago
የቡርኪናፋሶ መንግስት በቢል ጌትስ የሚደገፈው የወባ መከላከያ ፕሮጀክት ላይ እገዳ ጣለ፡፡ በካፒቴን_ኢብራሂም_ትራኦሬ የሚመራው የቡርኪናፋሶ መንግስት ታርጌት_ማላሪያ›› በተሰኘው በቢል ጌትስ የገንዘብ ድጋፍ በሚንቀሳቀሰው የወባ ምርምር ፕሮጀክት ላይ እገዳ መጣሉን አስታወቀ፡፡
ይህ ፕሮጀክት ወባን ለመከላከል በሚል በቴክኖሎጂ የተለወጡ ወይንም የጂኤምኦ የወባ ትንኞችን የሚያመርት ነው፡፡ የቡርኪናፋሶ ትምህርትና ምርምር ሚኒስትር ባወጣው መግለጫ ይህ ፕሮጀክት በአስቸኳይ ስራውን እንዲያቆም መታዘዙን አስታውቋል፡፡
በፕሮጀክቱ አማካኝነት የተመረቱትና በመጋዘን ውስጥ የሚገኙት የወባ ትንኞችም ፕሮቶኮሉን በጠበቀ ሁኔታ እንዲወገዱ ያሳሰበው ሚኒስትሩ ይህ ፕሮጀክት በመላው አገሪቱ ውስጥ የሚያደርገውን ማንኛውንም እንቅስቃሴ እንዲያቆምም ጥብቅ ማስጠንቀቂያ ሰጥቷል፡፡ ታርጌት ማለሪያ በቡርኪናፋሶ ስራ የጀመረው እ.ኤ.አ በ2012 ሲሆን አላማውም ዘረልውጥ የሆኑ የወባ ትንኞችን እያመረተ ወደበረሀ በመልቀቅ የወባ ስርጭትን መከላከል ነው፡፡
ይህ ታርጌት ማላሪያ ፕሮጀክት ለህብረተሰብ ጤና እጅግ ጎጂ እና የሚሰራበት መንገድ ለአካባቢው ማህበረሰብ የደህንነት ስጋት ነው ስትል ቡርኪናፋሶ ትችት አቅርባለች።
Seledadotio
Seledadotio
ይህ ፕሮጀክት ወባን ለመከላከል በሚል በቴክኖሎጂ የተለወጡ ወይንም የጂኤምኦ የወባ ትንኞችን የሚያመርት ነው፡፡ የቡርኪናፋሶ ትምህርትና ምርምር ሚኒስትር ባወጣው መግለጫ ይህ ፕሮጀክት በአስቸኳይ ስራውን እንዲያቆም መታዘዙን አስታውቋል፡፡
በፕሮጀክቱ አማካኝነት የተመረቱትና በመጋዘን ውስጥ የሚገኙት የወባ ትንኞችም ፕሮቶኮሉን በጠበቀ ሁኔታ እንዲወገዱ ያሳሰበው ሚኒስትሩ ይህ ፕሮጀክት በመላው አገሪቱ ውስጥ የሚያደርገውን ማንኛውንም እንቅስቃሴ እንዲያቆምም ጥብቅ ማስጠንቀቂያ ሰጥቷል፡፡ ታርጌት ማለሪያ በቡርኪናፋሶ ስራ የጀመረው እ.ኤ.አ በ2012 ሲሆን አላማውም ዘረልውጥ የሆኑ የወባ ትንኞችን እያመረተ ወደበረሀ በመልቀቅ የወባ ስርጭትን መከላከል ነው፡፡
ይህ ታርጌት ማላሪያ ፕሮጀክት ለህብረተሰብ ጤና እጅግ ጎጂ እና የሚሰራበት መንገድ ለአካባቢው ማህበረሰብ የደህንነት ስጋት ነው ስትል ቡርኪናፋሶ ትችት አቅርባለች።
Seledadotio
Seledadotio
9 months ago
በኢብራሂም ትራኦሬ አገር ቡርኪናፋሶ
ባህላዊ መሪዎች በፖለቲካ ውስጥ እንዲሳተፉ አይፈቀድም
#ethiopia | በኢብራሂም ትራኦሬ አገር ባህላዊ ወይም ልማዳዊ መሪዎች፣ በፖለቲካ ውስጥ እንዳይሳተፉ ተከልክለዋል፡፡ የግድ በፖለቲካ ውስጥ መሳተፍ ካለባቸውም ከባህላዊ የአመራር ሚናቸው መልቀቅ አለባቸው፡፡
እ.ኤ.አ. በ2025 መጀመሪያ ላይ የቡርኪናፋሶ መንግስት በሀገሪቱ የህግ መዋቅር ውስጥ ለልማዳዊና ባህላዊ አለቆች በይፋ እውቅና የሚሰጥ ህግ አውጥቷል። ይሁን እንጂ ሕጉ አንድ ጉልህ ድንጋጌን ያካትታል፡ በፖለቲካ ውስጥ መሳተፍ የሚፈልጉ የጎሳ አለቆች ከልማዳዊ ወይም ባሕላዊ ሃላፊነታቸው መልቀቃቸው አለባቸው።
ባህላዊና ልማዳዊ መሪዎች ህጋዊ እውቅና ያገኙት በአካባቢው ማህበረሰቦች መካከል ሰላምና አንድነት እንዲሰፍን ሚናቸውን ለማጠናከር በማለም ነው ተብሏል፡፡
ባህላዊ የጎሳ መሪዎች በፖለቲካ ውስጥ መሳተፍ ከፈለጉ ባህላዊ ሚናቸውን መተው ይኖርባቸዋል፡፡ ሁለቱንም ሚናዎች በአንድ ጊዜ መያዝን ህጉ አይፈቅድም፡፡
መንግስት ይህን ያደረገው ባህላዊ አመራርን ከወገንተኝነት ፖለቲካ ለመነጠል፣ የባህላዊ አለቆችን ሞራልና አንድነትን የማስጠበቅ ሚና ለማስቀጠል እንዲሁም የፖለቲካ ስልጣን ከያዙ ሊነሱ የሚችሉ የጥቅም ግጭቶችን ለመከላከል ነው ተብሏል።
ባህላዊ መሪዎች በፖለቲካ ውስጥ እንዲሳተፉ አይፈቀድም
#ethiopia | በኢብራሂም ትራኦሬ አገር ባህላዊ ወይም ልማዳዊ መሪዎች፣ በፖለቲካ ውስጥ እንዳይሳተፉ ተከልክለዋል፡፡ የግድ በፖለቲካ ውስጥ መሳተፍ ካለባቸውም ከባህላዊ የአመራር ሚናቸው መልቀቅ አለባቸው፡፡
እ.ኤ.አ. በ2025 መጀመሪያ ላይ የቡርኪናፋሶ መንግስት በሀገሪቱ የህግ መዋቅር ውስጥ ለልማዳዊና ባህላዊ አለቆች በይፋ እውቅና የሚሰጥ ህግ አውጥቷል። ይሁን እንጂ ሕጉ አንድ ጉልህ ድንጋጌን ያካትታል፡ በፖለቲካ ውስጥ መሳተፍ የሚፈልጉ የጎሳ አለቆች ከልማዳዊ ወይም ባሕላዊ ሃላፊነታቸው መልቀቃቸው አለባቸው።
ባህላዊና ልማዳዊ መሪዎች ህጋዊ እውቅና ያገኙት በአካባቢው ማህበረሰቦች መካከል ሰላምና አንድነት እንዲሰፍን ሚናቸውን ለማጠናከር በማለም ነው ተብሏል፡፡
ባህላዊ የጎሳ መሪዎች በፖለቲካ ውስጥ መሳተፍ ከፈለጉ ባህላዊ ሚናቸውን መተው ይኖርባቸዋል፡፡ ሁለቱንም ሚናዎች በአንድ ጊዜ መያዝን ህጉ አይፈቅድም፡፡
መንግስት ይህን ያደረገው ባህላዊ አመራርን ከወገንተኝነት ፖለቲካ ለመነጠል፣ የባህላዊ አለቆችን ሞራልና አንድነትን የማስጠበቅ ሚና ለማስቀጠል እንዲሁም የፖለቲካ ስልጣን ከያዙ ሊነሱ የሚችሉ የጥቅም ግጭቶችን ለመከላከል ነው ተብሏል።
10 months ago
ቻይና ቡርኪናፋሶን ዘመናዊ መሳሪያ አስታጠቀች !
ቻይና ከምዕራባዉያን ጋር ባላት አለመግባባት በተጣሉባት ማዕቀብ የአቅርቦት ችግር ለገጠማት ቡርኪናፋሶ የታጠቁ ተሽከርካሪዎችን ፣ መድፍ ስርዓቶችን ሽጉጦች-ሞርታሮችን እና SR5 ሮኬት ስርዓቶችን ማስታጠቋ ተሰማ ።
ይህ የቻይና ተግባርም ለበርካታ አመታት በኔቶ አባል ሀገራት ስር የቆየዉን የአፍሪካ የጦር መሳርያ ትጥቅ
አማራጭና የቤጂንግ የመከላከያ ኢንዱስትሪ በአህጉሩ ያለዉን ተፅዕኖ የሚያሳይ ተብሏል ።
የተሰሩ የታጠቁ ተሽከርካሪዎችን እና የጦር መሳሪያ መሳሪያዎችን በማጓጓዝ በአፍሪካ ወታደሮች መካከል ወደ ቤጂንግ የመከላከያ ኢንዱስትሪ እየጨመረ ያለውን ለውጥ ያሳያል ።
ቡርኪና ፋሶ መከላከያን አሻሽሏል በቻይና-የተሰራ የታጠቁ ተሽከርካሪዎችን ፣ መድፍ ስርዓቶችን
ቡርኪና ፋሶ በቻይና-የተሰራ የታጠቁ ተሽከርካሪዎችን ፣ የመድፍ ስርዓቶችን በማቅረብ መከላከያን ያሻሽላል
ቡርኪና ፋሶ ወደ መቀየሩን የሚያመላክት በቻይና የተሰሩ የታጠቁ ተሽከርካሪዎችን እና የጦር መሳሪያዎችን ተቀብላለች።
ምንም እንኳን የቡርኪናፋሶ መከላከያ ሚኒስቴር በስጦታ ይሁን በግዥ ባይገልጽም ካፒቴን ኢብራሂም ትራኦሬ ከቻይና የሚደረጉ ድጋፎችና ለሳህል ቀጠና ባለብዙ ደረጃ የዘመናዊ መሳርያ የማስታጠቅ ተግባር የዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት አካል መሆኑን ከዚህ ቀደም አረጋግጠዋል።
ከዚህ ቀደምም በሰኔ 2024 ቡርኪናፋሶ CS/VP14 እና VP11 ፈንጂ የሚቋቋሙ ለድብቅ ጥበቃ (ኤምአርኤፒ) የሚሆኑ ተሽከርርካሪዎችን ጨምሮ የቻይና ስሪት ዘመናዊ መሳርያዎችን ለዘመናዊነት ፕሮግራም መቀበሏን ወታደራዊ አፍሪካ ዘግቧል።
የቡርኪና ፋሶን ደህንነት ለማስጠበቅና ለመከላከያ በሚል ቻይና በቤጂንግ የመከላከያ ኢንደስትሪ የተሰሩ የታጠቁ ተሽከርካሪዎችን እና የጦር መሳሪያዎችን አበርክታለች ሲል የዘገበው ቢዝነስ ኢንሳይደር የዜና ወኪል ነዉ ።
እንደ ዘገባው ከሆነ በርካታ የመድፍ ስርዓቶችን
የVN22B የዉጊያ ተሽከርካሪዎችን፣ PLL-05 ሽጉጥ-ሞርታሮችን እና SR5 ሮኬት ስርዓቶችን ያካትታል፣ ይህም ከምዕራባዉያን ጋር ሆድና ጀርባ እየሆነች ለምትገኘዉና የአሸባሪዎች እንቅስቃሴ መፈንቅለ መንግስት ሙከራ እየናጣት ለምትገኘዉ ቡርኪናፋሶ ሃይሏን ለማጠናከር የሚረዳ ነዉ ተብሏል ።
የቻይና ወታደራዊ መሳሪያዎች በዋጋቸዉ እርካሽነት በፈጣን አቅርቦት እና በተለዋዋጭ የፋይናንስ አማራጮች ምክንያት በአፍሪካ ውስጥ በተወዳዳሪና ተወዳጅነትን እያገኙ ይገኛል ያለዉ ዘገባው ለአብነትም በኮትዲር፣ በጋቦን፣ በማሊ እና በኬንያ ጠንካራ ይዞታ ያላቸው የቻይና ወታደራዊ መሳሪያዎች በብዛት እያገለገሉና በመላው አፍሪካም በብዛት እየታዩ መጥተዋል። ብሏል ።
የኔታ ቲዩብ ዘጋቢ ፦ ታዴ የማመይ ልጅ
ቻይና ከምዕራባዉያን ጋር ባላት አለመግባባት በተጣሉባት ማዕቀብ የአቅርቦት ችግር ለገጠማት ቡርኪናፋሶ የታጠቁ ተሽከርካሪዎችን ፣ መድፍ ስርዓቶችን ሽጉጦች-ሞርታሮችን እና SR5 ሮኬት ስርዓቶችን ማስታጠቋ ተሰማ ።
ይህ የቻይና ተግባርም ለበርካታ አመታት በኔቶ አባል ሀገራት ስር የቆየዉን የአፍሪካ የጦር መሳርያ ትጥቅ
አማራጭና የቤጂንግ የመከላከያ ኢንዱስትሪ በአህጉሩ ያለዉን ተፅዕኖ የሚያሳይ ተብሏል ።
የተሰሩ የታጠቁ ተሽከርካሪዎችን እና የጦር መሳሪያ መሳሪያዎችን በማጓጓዝ በአፍሪካ ወታደሮች መካከል ወደ ቤጂንግ የመከላከያ ኢንዱስትሪ እየጨመረ ያለውን ለውጥ ያሳያል ።
ቡርኪና ፋሶ መከላከያን አሻሽሏል በቻይና-የተሰራ የታጠቁ ተሽከርካሪዎችን ፣ መድፍ ስርዓቶችን
ቡርኪና ፋሶ በቻይና-የተሰራ የታጠቁ ተሽከርካሪዎችን ፣ የመድፍ ስርዓቶችን በማቅረብ መከላከያን ያሻሽላል
ቡርኪና ፋሶ ወደ መቀየሩን የሚያመላክት በቻይና የተሰሩ የታጠቁ ተሽከርካሪዎችን እና የጦር መሳሪያዎችን ተቀብላለች።
ምንም እንኳን የቡርኪናፋሶ መከላከያ ሚኒስቴር በስጦታ ይሁን በግዥ ባይገልጽም ካፒቴን ኢብራሂም ትራኦሬ ከቻይና የሚደረጉ ድጋፎችና ለሳህል ቀጠና ባለብዙ ደረጃ የዘመናዊ መሳርያ የማስታጠቅ ተግባር የዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት አካል መሆኑን ከዚህ ቀደም አረጋግጠዋል።
ከዚህ ቀደምም በሰኔ 2024 ቡርኪናፋሶ CS/VP14 እና VP11 ፈንጂ የሚቋቋሙ ለድብቅ ጥበቃ (ኤምአርኤፒ) የሚሆኑ ተሽከርርካሪዎችን ጨምሮ የቻይና ስሪት ዘመናዊ መሳርያዎችን ለዘመናዊነት ፕሮግራም መቀበሏን ወታደራዊ አፍሪካ ዘግቧል።
የቡርኪና ፋሶን ደህንነት ለማስጠበቅና ለመከላከያ በሚል ቻይና በቤጂንግ የመከላከያ ኢንደስትሪ የተሰሩ የታጠቁ ተሽከርካሪዎችን እና የጦር መሳሪያዎችን አበርክታለች ሲል የዘገበው ቢዝነስ ኢንሳይደር የዜና ወኪል ነዉ ።
እንደ ዘገባው ከሆነ በርካታ የመድፍ ስርዓቶችን
የVN22B የዉጊያ ተሽከርካሪዎችን፣ PLL-05 ሽጉጥ-ሞርታሮችን እና SR5 ሮኬት ስርዓቶችን ያካትታል፣ ይህም ከምዕራባዉያን ጋር ሆድና ጀርባ እየሆነች ለምትገኘዉና የአሸባሪዎች እንቅስቃሴ መፈንቅለ መንግስት ሙከራ እየናጣት ለምትገኘዉ ቡርኪናፋሶ ሃይሏን ለማጠናከር የሚረዳ ነዉ ተብሏል ።
የቻይና ወታደራዊ መሳሪያዎች በዋጋቸዉ እርካሽነት በፈጣን አቅርቦት እና በተለዋዋጭ የፋይናንስ አማራጮች ምክንያት በአፍሪካ ውስጥ በተወዳዳሪና ተወዳጅነትን እያገኙ ይገኛል ያለዉ ዘገባው ለአብነትም በኮትዲር፣ በጋቦን፣ በማሊ እና በኬንያ ጠንካራ ይዞታ ያላቸው የቻይና ወታደራዊ መሳሪያዎች በብዛት እያገለገሉና በመላው አፍሪካም በብዛት እየታዩ መጥተዋል። ብሏል ።
የኔታ ቲዩብ ዘጋቢ ፦ ታዴ የማመይ ልጅ
Sponsored by
Surafel
10 months ago
በኢብራሂም ትራኦሬ ላይ አፈሙዝ አነሱበት !
የአልቃይዳ ቅርንጫፍ የሆነው ጀማአት ኑስራት አል ኢስላም ዋል ሙስሊም (ጄኒም) በሰሜናዊ ቡርኪናፋሶ በሚገኝ ወታደራዊ ካምፕ ላይ በታጣቂዎች በተፈፀመ ጥቃት 50 የሚጠጉ ወታደሮች መሞታቸውን የማህበረሰብ መሪ እና ነዋሪዎች ተናገሩ ።
እንደዘገባው ከሆነ ይህን ጥቃት በምዕራብ አፍሪካ ዙሪያ ጥቃቶችን ከሚፈጽሙ በርካታ የታጠቁ ቡድኖች አንዱ የሆነው JNIM ናስር አል እስላም ዋል ቡድን እንደፈፀሙት ተገልጿል ።
ለዘመናት በመፈንቅለ መንግስት ስትናጥ የቆየችው ቡርኪናፋሶ የወታደራዊው መሪ ኢብራሂም ትራኦሬ ከመጣ በኋላ የተሻለ እድገትና ለዉጥ የፖለቲካ እና የወታደራዊ አጋሮችን እንደገና ቢያደርግም JNIM እስላማዊ ቡድኖችን መቆጣጠር አልቻለም ያለዉ የአሶሽት ፕረስ ዘገባ ሁለቱ ምንጮች በመጥቀስ በሰራው ዜና ቡድኑ የምዕራብ አፍሪካ ሰሜናዊ ክልል ዳርጎ በሚገኘው ቦልሳ ግዛት ሰኞ ላይ በፈፀመው ጥቃት 100 የሚጠጉ ታጣቂዎች መሣተፋቸውን እና ታጣቂዎቹ ግድያው ከተፈፀሙ በኋላ ተቋማትን አቃጥለው ዘርፈዋል። ብሏል ።
በምዕራባውያን አስተባባሪነትና አስታጣቂነት ቡርኪናፋሶ አብዛኛዉን የሀገሪቱን ክፍል በተለይም ከመዲናይቱ ዉጭ ጥቃቶች ተበራክተዋል በንፁሃን ላይም የታጣቂ ቡድኖች ጥቃት እየደረሰ ነዉ።ሲል አክሏል አሶሼትድ ፕሬስ ።
በማሊ ቡርኪናፋሶ አካባቢ የሚገኘው የአልቃይዳ ቅርንጫፍ የሆነው ጀማአት ኑስራት አል ኢስላም ዋል ሙስሊም (ጄኒም) በኦፊሴላዊው የሚዲያ አካል አዝ-ዛላካ በኩል ባሰፈረው መረጃዎች የሳህል አካባቢ እስላማዊ መንግስት የመመስረት አላማ እንዳለው ከድህረገፁ ያገኘነው መረጃ ያሳያል ።
የኔታ ቲዩብ ዘጋቢ ፦ ታዴ የማመይ ልጅ
የአልቃይዳ ቅርንጫፍ የሆነው ጀማአት ኑስራት አል ኢስላም ዋል ሙስሊም (ጄኒም) በሰሜናዊ ቡርኪናፋሶ በሚገኝ ወታደራዊ ካምፕ ላይ በታጣቂዎች በተፈፀመ ጥቃት 50 የሚጠጉ ወታደሮች መሞታቸውን የማህበረሰብ መሪ እና ነዋሪዎች ተናገሩ ።
እንደዘገባው ከሆነ ይህን ጥቃት በምዕራብ አፍሪካ ዙሪያ ጥቃቶችን ከሚፈጽሙ በርካታ የታጠቁ ቡድኖች አንዱ የሆነው JNIM ናስር አል እስላም ዋል ቡድን እንደፈፀሙት ተገልጿል ።
ለዘመናት በመፈንቅለ መንግስት ስትናጥ የቆየችው ቡርኪናፋሶ የወታደራዊው መሪ ኢብራሂም ትራኦሬ ከመጣ በኋላ የተሻለ እድገትና ለዉጥ የፖለቲካ እና የወታደራዊ አጋሮችን እንደገና ቢያደርግም JNIM እስላማዊ ቡድኖችን መቆጣጠር አልቻለም ያለዉ የአሶሽት ፕረስ ዘገባ ሁለቱ ምንጮች በመጥቀስ በሰራው ዜና ቡድኑ የምዕራብ አፍሪካ ሰሜናዊ ክልል ዳርጎ በሚገኘው ቦልሳ ግዛት ሰኞ ላይ በፈፀመው ጥቃት 100 የሚጠጉ ታጣቂዎች መሣተፋቸውን እና ታጣቂዎቹ ግድያው ከተፈፀሙ በኋላ ተቋማትን አቃጥለው ዘርፈዋል። ብሏል ።
በምዕራባውያን አስተባባሪነትና አስታጣቂነት ቡርኪናፋሶ አብዛኛዉን የሀገሪቱን ክፍል በተለይም ከመዲናይቱ ዉጭ ጥቃቶች ተበራክተዋል በንፁሃን ላይም የታጣቂ ቡድኖች ጥቃት እየደረሰ ነዉ።ሲል አክሏል አሶሼትድ ፕሬስ ።
በማሊ ቡርኪናፋሶ አካባቢ የሚገኘው የአልቃይዳ ቅርንጫፍ የሆነው ጀማአት ኑስራት አል ኢስላም ዋል ሙስሊም (ጄኒም) በኦፊሴላዊው የሚዲያ አካል አዝ-ዛላካ በኩል ባሰፈረው መረጃዎች የሳህል አካባቢ እስላማዊ መንግስት የመመስረት አላማ እንዳለው ከድህረገፁ ያገኘነው መረጃ ያሳያል ።
የኔታ ቲዩብ ዘጋቢ ፦ ታዴ የማመይ ልጅ
11 months ago
ትራኦሬ የምርጫ ኮሚሽንን በተኑ፡ የቡርኪናፋሶ ምርጫ ሂደት በእጅጉ ተቀይሯል
በካፒቴን ኢብራሂም ትራኦሬ የሚመራው የቡርኪናፋሶ ወታደራዊ መንግስት የሀገሪቱን ብሔራዊ ነጻ የምርጫ ኮሚሽን (CENI) መበተኑን ይፋ አድርጓል። ቢቢሲ እንደዘገበው ከሆነ ለዚህ ውሳኔ ዋነኛው ምክንያት ኮሚሽኑ ከፍተኛ የገንዘብ ብክነት በማሳየቱ ነው።
ከዚህ በኋላ በቀጣይ የሚደረጉ ምርጫዎችን የማስፈጸም ኃላፊነት ለሀገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስቴር ተሰጥቷል። ወታደራዊ መሪዎቹ ይህ እርምጃ ገንዘብን ከመቆጠብ ባለፈ፣ ሀገሪቱ በምርጫ ሂደቱ ላይ ያላትን ሉዓላዊ ቁጥጥር እንደሚያጠናክርና የውጭ ተጽዕኖዎችን እንደሚገድብ ያምናሉ።
ይህ የካፒቴን ትራኦሬ መንግስት የወሰደው እርምጃ በቡርኪናፋሶ የምርጫ ስርዓት ላይ ትልቅ ለውጥ የሚያመጣ ሲሆን፣ በሀገሪቱ የፖለቲካ ምህዳር ላይም የራሱ የሆነ ተጽዕኖ ይኖረዋል። በቀጣይ በሚካሄዱ ምርጫዎች የሀገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስቴር አዲስ ሚና ምን እንደሚመስል የሚታይ ይሆናል።
Seledadotio
Seledadotio
በካፒቴን ኢብራሂም ትራኦሬ የሚመራው የቡርኪናፋሶ ወታደራዊ መንግስት የሀገሪቱን ብሔራዊ ነጻ የምርጫ ኮሚሽን (CENI) መበተኑን ይፋ አድርጓል። ቢቢሲ እንደዘገበው ከሆነ ለዚህ ውሳኔ ዋነኛው ምክንያት ኮሚሽኑ ከፍተኛ የገንዘብ ብክነት በማሳየቱ ነው።
ከዚህ በኋላ በቀጣይ የሚደረጉ ምርጫዎችን የማስፈጸም ኃላፊነት ለሀገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስቴር ተሰጥቷል። ወታደራዊ መሪዎቹ ይህ እርምጃ ገንዘብን ከመቆጠብ ባለፈ፣ ሀገሪቱ በምርጫ ሂደቱ ላይ ያላትን ሉዓላዊ ቁጥጥር እንደሚያጠናክርና የውጭ ተጽዕኖዎችን እንደሚገድብ ያምናሉ።
ይህ የካፒቴን ትራኦሬ መንግስት የወሰደው እርምጃ በቡርኪናፋሶ የምርጫ ስርዓት ላይ ትልቅ ለውጥ የሚያመጣ ሲሆን፣ በሀገሪቱ የፖለቲካ ምህዳር ላይም የራሱ የሆነ ተጽዕኖ ይኖረዋል። በቀጣይ በሚካሄዱ ምርጫዎች የሀገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስቴር አዲስ ሚና ምን እንደሚመስል የሚታይ ይሆናል።
Seledadotio
Seledadotio
11 months ago
የቡርኪናፋሶ ወታደራዊ መሪዎች የአገሪቱን ምርጫ ኮሚሽን አፈረሱ
የቡርኪናፋሶ ወታደራዊ መሪዎች የአገሪቱን የምርጫ ኮሚሽን የገንዘብ ብክነት ነው በሚል በተኑ።
የአገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስቴር ወደፊት የሚደረገውን ምርጫ እንደሚያስተባብር የአገሪቱ ብሔራዊ የቴሌቪዥን ጣቢያ አርቲቢ ዘግቧል።
እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ2022 መስከረም ወር በመፈንቅለ መንግሥት የአገሪቱን ሥልጣን የተቆጣጠሩት አመራሮች በአገሪቱ የተለያዩ ማሻሻያዎችን ማድረግ ጀምረዋል።
የማሻሻያዎቹ አካል ከሆኑት መካከል ወደ የሲቪል አስተዳደር የሚወስደውን ምርጫ ማራዘምን ያካትታል።
በአገር አቀፍ ደረጃ ምርጫ መካሄድ የነበረበት ባለፈው ዓመት ቢሆንም ወታደራዊ አመራሮች አገሪቱ ወደ ዲሞክራሲ የምታደርገውን ሽግግር እስከ ሐምሌ 2029 ድረስ አራዝመዋል
። ይህም መሪው ኢብራሂም ትራኦሬ በሥልጣን ላይ እንዲቆዩ እና በሚቀጥለው ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ ያለ ተቀናቃኝ እንዲወዳደሩ ያስችላቸዋል።
የኤኤፍፒ የዜና ወኪል የጋዝት አስተዳደር ሚኒስትር ኤሚሌ ዜርቦን ጠቅሶ እንደዘገበው የምርጫ ኮሚሽኑ በዓመት 870,000 ዶላር የሚጠጋ ገንዘብ ድጎማ ተደርጎለታል።
ሚኒስትሩ ኮሚሽኑን ማፍረስ "በምርጫ ሂደቱ ላይ ያለንን ሉዓላዊ ቁጥጥር እንደሚያጠናክር እና በተመሳሳይ የውጭ ተጽዕኖዎችን ይገድባል" ብለዋል።
ከሦስት ዓመታት በፊት ወታደራዊ አመራሮቹ ወደ ሥልጣን ሲመጡ የሲቪል ባለስልጣናቱ እየጨመረ የመጣውን እስላማዊ አማጽያን መቋቋም አልቻሉም በሚል ተችተው ነበር።
በወቅቱ የወታደራዊ መሪዎቹ ከቀድሞ ቅኝ ገዢዋ ፈረንሳይ የምትሰጠውን እርዳታ አንቀበልም ሲሉ ውድቅ አድርገዋል።
የመብት ተሟጋቾች ሠራዊቱ ታጣቂዎቹን ለመደምሰስ ባደረገው ሙከራ በሰላማዊ ሰዎች ላይ አነጣጥሯል ሲሉ፣ የፖለቲካ እንቅስቃሴን እና ሃሳብን በነጻነት የመግለጽ መብትን በማፈን ይከስሷቸዋል።
በወታደራዊ ዘመቻው ውጤታማነት ላይ በርካታ ጥያቄዎች ይነሳሉ።
በ2025 የመጀመሪያ አጋማሽ ላይ የጂሃዲስት ቡድን ጄኤንአይኤም በቡርኪናፋሶ ውስጥ ከ280 በላይ ጥቃቶችን መፈፀሙን ተናግሯል።
ቢቢሲ ባረጋገጠው መረጃ መሰረት ቡድኑ የሚፈጽመው ጥቃት በ2024 ከነበረው በእጥፍ አድጓል።
እ.ኤ.አ. በ 2022 በመፈንቅለ መንግሥት ሥልጣኑን ከተቆጣጠረ በኋላ፣ የትራኦሬ አገዛዝ የቀድሞ የቡርኪናፋሶን ቅኝ ገዢ ፈረንሳይን ምትክ ከሩሲያ ጋር ጠንካራ ወዳጅነት እንድትመሠርት አድርጓል።
BBC
የቡርኪናፋሶ ወታደራዊ መሪዎች የአገሪቱን የምርጫ ኮሚሽን የገንዘብ ብክነት ነው በሚል በተኑ።
የአገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስቴር ወደፊት የሚደረገውን ምርጫ እንደሚያስተባብር የአገሪቱ ብሔራዊ የቴሌቪዥን ጣቢያ አርቲቢ ዘግቧል።
እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ2022 መስከረም ወር በመፈንቅለ መንግሥት የአገሪቱን ሥልጣን የተቆጣጠሩት አመራሮች በአገሪቱ የተለያዩ ማሻሻያዎችን ማድረግ ጀምረዋል።
የማሻሻያዎቹ አካል ከሆኑት መካከል ወደ የሲቪል አስተዳደር የሚወስደውን ምርጫ ማራዘምን ያካትታል።
በአገር አቀፍ ደረጃ ምርጫ መካሄድ የነበረበት ባለፈው ዓመት ቢሆንም ወታደራዊ አመራሮች አገሪቱ ወደ ዲሞክራሲ የምታደርገውን ሽግግር እስከ ሐምሌ 2029 ድረስ አራዝመዋል
። ይህም መሪው ኢብራሂም ትራኦሬ በሥልጣን ላይ እንዲቆዩ እና በሚቀጥለው ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ ያለ ተቀናቃኝ እንዲወዳደሩ ያስችላቸዋል።
የኤኤፍፒ የዜና ወኪል የጋዝት አስተዳደር ሚኒስትር ኤሚሌ ዜርቦን ጠቅሶ እንደዘገበው የምርጫ ኮሚሽኑ በዓመት 870,000 ዶላር የሚጠጋ ገንዘብ ድጎማ ተደርጎለታል።
ሚኒስትሩ ኮሚሽኑን ማፍረስ "በምርጫ ሂደቱ ላይ ያለንን ሉዓላዊ ቁጥጥር እንደሚያጠናክር እና በተመሳሳይ የውጭ ተጽዕኖዎችን ይገድባል" ብለዋል።
ከሦስት ዓመታት በፊት ወታደራዊ አመራሮቹ ወደ ሥልጣን ሲመጡ የሲቪል ባለስልጣናቱ እየጨመረ የመጣውን እስላማዊ አማጽያን መቋቋም አልቻሉም በሚል ተችተው ነበር።
በወቅቱ የወታደራዊ መሪዎቹ ከቀድሞ ቅኝ ገዢዋ ፈረንሳይ የምትሰጠውን እርዳታ አንቀበልም ሲሉ ውድቅ አድርገዋል።
የመብት ተሟጋቾች ሠራዊቱ ታጣቂዎቹን ለመደምሰስ ባደረገው ሙከራ በሰላማዊ ሰዎች ላይ አነጣጥሯል ሲሉ፣ የፖለቲካ እንቅስቃሴን እና ሃሳብን በነጻነት የመግለጽ መብትን በማፈን ይከስሷቸዋል።
በወታደራዊ ዘመቻው ውጤታማነት ላይ በርካታ ጥያቄዎች ይነሳሉ።
በ2025 የመጀመሪያ አጋማሽ ላይ የጂሃዲስት ቡድን ጄኤንአይኤም በቡርኪናፋሶ ውስጥ ከ280 በላይ ጥቃቶችን መፈፀሙን ተናግሯል።
ቢቢሲ ባረጋገጠው መረጃ መሰረት ቡድኑ የሚፈጽመው ጥቃት በ2024 ከነበረው በእጥፍ አድጓል።
እ.ኤ.አ. በ 2022 በመፈንቅለ መንግሥት ሥልጣኑን ከተቆጣጠረ በኋላ፣ የትራኦሬ አገዛዝ የቀድሞ የቡርኪናፋሶን ቅኝ ገዢ ፈረንሳይን ምትክ ከሩሲያ ጋር ጠንካራ ወዳጅነት እንድትመሠርት አድርጓል።
BBC
11 months ago
ቡርኪናፋሶ የምዕራባውያን ተቋማት አገደች !
የቡርኪናፋሶው ፕሬዚዳንት ኢብራሂም ትራኦሬ ሀገሪቱን የማበጥበጥ ሰላም የመንሳት ማህበራዊ እረፍት የማሳጣት አላማ አላቸው ያሏቸውን አራት በምዕራባውያን እና አሜሪካ የሚመሩ መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶችን ፈቃዳቸውን መቀማቱን እና ሌሎች ሁለት ማህበራትን ማገዱ ተነገረ ።
እ.ኤ.አ. በሴፕቴምበር 2022 በተካሄደው መፈንቅለ መንግስት ስልጣኑን የተቆጣጠረው የቡርኪና ጦር ሃይል ከዚያን ጊዜ ጀምሮ የብሄራዊ ሉዓላዊነትን ማስመለስን ከቅድሚያ ጉዳዮች ውስጥ አንዱ በማድረግ በ"ግጭት " ተግባር የተከሰሱ ዲፕሎማቶች ከሀገር እንዲባረሩ ተደርገዋል፣በርካታ የውጭ ሚዲያዎችም ለመዝጋት ተገደዋል።
የወታደራዊው መንግስት ቀጣይነት ያለው የጸጥታ እርምጃዎች አካል የሆነዉና በሰኔ ወር አጋማሽ ላይ የሀገሪቱ ፍርድ ቤት ባወጣው ድንጋጌዎች መሰረት ሀገሪቱን ለብጥብጥ እና ግጭት ለመዳረግ እያሴሩ ነዉ ያሏቸውን አራት የውጭ መንግስታዊ ያልሆኑ ማኅበራት ለሶስት ወራት ታግደዋል፣ ሁለቱን በመረጃ ጥሰት ክስ በመመስረት ፍርድ ቤት አስቁመዋቸዋል ይህ እርምጃም ቀጣይነት እንዳለዉ አረጋግጫለሁ ሲል የመንግስት ሚኒስትርን ዋቢ በማድረግ የዘገበው አጃንስ ፍራንስ ፕሬስ ነዉ ።
የቡርኪናፋሶው ፕሬዚዳንት ኢብራሂም ትራኦሬ ሀገሪቱን የማበጥበጥ ሰላም የመንሳት ማህበራዊ እረፍት የማሳጣት አላማ አላቸው ያሏቸውን አራት በምዕራባውያን እና አሜሪካ የሚመሩ መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶችን ፈቃዳቸውን መቀማቱን እና ሌሎች ሁለት ማህበራትን ማገዱ ተነገረ ።
እ.ኤ.አ. በሴፕቴምበር 2022 በተካሄደው መፈንቅለ መንግስት ስልጣኑን የተቆጣጠረው የቡርኪና ጦር ሃይል ከዚያን ጊዜ ጀምሮ የብሄራዊ ሉዓላዊነትን ማስመለስን ከቅድሚያ ጉዳዮች ውስጥ አንዱ በማድረግ በ"ግጭት " ተግባር የተከሰሱ ዲፕሎማቶች ከሀገር እንዲባረሩ ተደርገዋል፣በርካታ የውጭ ሚዲያዎችም ለመዝጋት ተገደዋል።
የወታደራዊው መንግስት ቀጣይነት ያለው የጸጥታ እርምጃዎች አካል የሆነዉና በሰኔ ወር አጋማሽ ላይ የሀገሪቱ ፍርድ ቤት ባወጣው ድንጋጌዎች መሰረት ሀገሪቱን ለብጥብጥ እና ግጭት ለመዳረግ እያሴሩ ነዉ ያሏቸውን አራት የውጭ መንግስታዊ ያልሆኑ ማኅበራት ለሶስት ወራት ታግደዋል፣ ሁለቱን በመረጃ ጥሰት ክስ በመመስረት ፍርድ ቤት አስቁመዋቸዋል ይህ እርምጃም ቀጣይነት እንዳለዉ አረጋግጫለሁ ሲል የመንግስት ሚኒስትርን ዋቢ በማድረግ የዘገበው አጃንስ ፍራንስ ፕሬስ ነዉ ።