2 months ago
አዲስ ዓለም አቀፍ የቅድመ ክፍያ ቪዛ ካርድ ለአገልግሎት ክፍት ሆነ
#ethiopia | የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከኢትዮጵያ አየር መንገድ እና ከቪዛ ኩባንያ ጋር በመተባበር አዲስ ዓለም አቀፍ የክፍያ ካርድ በጋራ ይፋ ማድረጋቸውን አስታውቀዋል።
ይህ አዲስ የቪዛ ካርድ ደንበኞች ወደተለያዩ የዓለም ሀገራት በሚጓዙበት ወቅት የገንዘብ ክፍያዎችን በቀላሉ ለመፈጸም የሚያስችላቸው ሲሆን፣ ካርዱን በሚጠቀሙበት ጊዜም የሸባ ማይልስ ማበረታቻ ተጠቃሚ እንደሚሆኑ ተገልጿል።
አገልግሎቱን ለማግኘት ግን የሁለቱም ተቋማት ማለትም የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና የኢትዮጵያ አየር መንገድ ደንበኛ መሆን ያስፈልጋል።
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ ኤፍሬም መኩሪያ እንደገለጹት፣ የአሁኑ ዘመን የዲጂታል ክፍያ ሥርዓት በስፋት የሚፈልግ በመሆኑ ይህ ይፋ የተደረገው ዓለም አቀፍ ካርድ የባንኩን ደንበኞች የውጭ ሀገር የንግድና የገንዘብ ዝውውር በእጅጉ የሚያቀላጥፍ ነው።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ለማ ያደቻ በበኩላቸው፣ አየር መንገዱ የደንበኞቹን የአገልግሎት እርካታ ለማሳደግና አሠራሩን ዘመናዊ ለማድረግ ከተለያዩ ተቋማት ጋር በቅንጅት እየሠራ እንደሚገኝ ጠቅሰው፣ አዲሱ የክፍያ ካርድ የሁለቱንም አንጋፋ ተቋማት ደንበኞች በእጅጉ ተጠቃሚ እንደሚያደርግ ማብራራታቸውን አሚኮ በዘገባው አስፍሯል።
#የኢትዮጵያንግድባንክ #የኢትዮጵያአየርመንገድ #ቪዛካርድ #የዲጂታልክፍያ #የባንክአገልግሎት #የአየርጉዞ #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከኢትዮጵያ አየር መንገድ እና ከቪዛ ኩባንያ ጋር በመተባበር አዲስ ዓለም አቀፍ የክፍያ ካርድ በጋራ ይፋ ማድረጋቸውን አስታውቀዋል።
ይህ አዲስ የቪዛ ካርድ ደንበኞች ወደተለያዩ የዓለም ሀገራት በሚጓዙበት ወቅት የገንዘብ ክፍያዎችን በቀላሉ ለመፈጸም የሚያስችላቸው ሲሆን፣ ካርዱን በሚጠቀሙበት ጊዜም የሸባ ማይልስ ማበረታቻ ተጠቃሚ እንደሚሆኑ ተገልጿል።
አገልግሎቱን ለማግኘት ግን የሁለቱም ተቋማት ማለትም የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና የኢትዮጵያ አየር መንገድ ደንበኛ መሆን ያስፈልጋል።
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ ኤፍሬም መኩሪያ እንደገለጹት፣ የአሁኑ ዘመን የዲጂታል ክፍያ ሥርዓት በስፋት የሚፈልግ በመሆኑ ይህ ይፋ የተደረገው ዓለም አቀፍ ካርድ የባንኩን ደንበኞች የውጭ ሀገር የንግድና የገንዘብ ዝውውር በእጅጉ የሚያቀላጥፍ ነው።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ለማ ያደቻ በበኩላቸው፣ አየር መንገዱ የደንበኞቹን የአገልግሎት እርካታ ለማሳደግና አሠራሩን ዘመናዊ ለማድረግ ከተለያዩ ተቋማት ጋር በቅንጅት እየሠራ እንደሚገኝ ጠቅሰው፣ አዲሱ የክፍያ ካርድ የሁለቱንም አንጋፋ ተቋማት ደንበኞች በእጅጉ ተጠቃሚ እንደሚያደርግ ማብራራታቸውን አሚኮ በዘገባው አስፍሯል።
#የኢትዮጵያንግድባንክ #የኢትዮጵያአየርመንገድ #ቪዛካርድ #የዲጂታልክፍያ #የባንክአገልግሎት #የአየርጉዞ #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
3 months ago
ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የተሰጠ አስቸኳይ መግለጫ!
* የታገዱ ሂሳቦች መፍትሄ አገኙ
#ethiopia | ለተከበራችሁ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ (CBE) ውድ ደንበኞች በሙሉ፤ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ መመሪያ መሠረት፣ በተመረጡ ከተሞች የሚገኙና ከ"ፋይዳ" መታወቂያ ጋር ያልተሳሰሩ የባንክ ሂሳቦች ላይ ተጥሎ የነበረው የእንቅስቃሴ እገዳን በተመለከተ ባንኩ አዲስና ፈጣን መፍትሄዎችን የያዘ መግለጫ አውጥቷል።
የእገዳው መነሻና አዲሱ መፍትሄ
እስከ ግንቦት 06 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ የፋይዳ መታወቂያ ቁጥራቸውን ከባንክ ሂሳባቸው ጋር ያላስተሳሰሩ ደንበኞች ሂሳባቸው እንዳይንቀሳቀስ ተደርጎ መቆየቱ ይታወሳል።
ይህንን ተከትሎ የደረሰውን ከፍተኛ የደንበኞች ጫና ለመቋቋም ባንኩ የሚከተሉትን እርምጃዎች ወስዷል፦
1. የታገዱ ሂሳቦች መለቀቅ
ከግንቦት 7 እስከ ግንቦት 12 ቀን ድረስ በእገዳ ምክንያት እንዳይንቀሳቀሱ ከተደረጉት ሂሳቦች ውጪ፣ የፋይዳ መታወቂያቸውን ያስተሳሰሩ ደንበኞች ሂሳባቸውን ወዲያውኑ ማንቀሳቀስ እንዲችሉ ተደርጓል።
2. አውቶማቲክ እገዳ ማንሳት
ከግንቦት 12 ጀምሮ ደንበኞች የፋይዳ መታወቂያቸውን ከሂሳባቸው ጋር እንዳስተሳሰሩ፣ የባንኩ የመረጃ ስርዓት (System) **በራሱ ጊዜ እገዳውን እንዲያነሳ** ተደርጓል።
አዲስ የቀነ-ገደብ ማሳሰቢያ
እስካሁን ያላስተሳሰሩ እና በሌሎች የሀገሪቱ ክፍሎች የሚገኙ ደንበኞች፣ የፋይዳ መታወቂያቸውን እስከ ሰኔ 30 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ በማስተሳሰር ሂሳባቸውን በቀጣይነት ማንቀሳቀስ እንዲችሉ ባንኩ በጥብቅ አሳስቧል።
የማስተሳሰሪያ አማራጮች፦
በማንኛውም የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ቅርንጫፍ በአካል በመገኘት።
በባንኩ የበይነ መረብ (Online) ማስተሳሰሪያ አማራጭ፦ 👉 https://cbefayda.cbe.com.e...
ባንኩ ደንበኞች በመጉላላታቸው ይቅርታ የጠየቀ ሲሆን፣ የደንበኞችን እርካታ እውን ለማድረግ መስራቱን እንደሚቀጥል አረጋግጧል።
#getu #cbe #commercialbankofethiopia #nationalid #faydaid #bankblockethiopia #onlineregistration #systemupdate #customersatisfaction #ሰበርዜና #ኢትዮጵያንግድባንክ #ፋይዳመታወቂያ #የባንክእገዳ #የዲጂታልኢትዮጵያ #ጌጡተመስገን #getutemesgen
* የታገዱ ሂሳቦች መፍትሄ አገኙ
#ethiopia | ለተከበራችሁ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ (CBE) ውድ ደንበኞች በሙሉ፤ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ መመሪያ መሠረት፣ በተመረጡ ከተሞች የሚገኙና ከ"ፋይዳ" መታወቂያ ጋር ያልተሳሰሩ የባንክ ሂሳቦች ላይ ተጥሎ የነበረው የእንቅስቃሴ እገዳን በተመለከተ ባንኩ አዲስና ፈጣን መፍትሄዎችን የያዘ መግለጫ አውጥቷል።
የእገዳው መነሻና አዲሱ መፍትሄ
እስከ ግንቦት 06 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ የፋይዳ መታወቂያ ቁጥራቸውን ከባንክ ሂሳባቸው ጋር ያላስተሳሰሩ ደንበኞች ሂሳባቸው እንዳይንቀሳቀስ ተደርጎ መቆየቱ ይታወሳል።
ይህንን ተከትሎ የደረሰውን ከፍተኛ የደንበኞች ጫና ለመቋቋም ባንኩ የሚከተሉትን እርምጃዎች ወስዷል፦
1. የታገዱ ሂሳቦች መለቀቅ
ከግንቦት 7 እስከ ግንቦት 12 ቀን ድረስ በእገዳ ምክንያት እንዳይንቀሳቀሱ ከተደረጉት ሂሳቦች ውጪ፣ የፋይዳ መታወቂያቸውን ያስተሳሰሩ ደንበኞች ሂሳባቸውን ወዲያውኑ ማንቀሳቀስ እንዲችሉ ተደርጓል።
2. አውቶማቲክ እገዳ ማንሳት
ከግንቦት 12 ጀምሮ ደንበኞች የፋይዳ መታወቂያቸውን ከሂሳባቸው ጋር እንዳስተሳሰሩ፣ የባንኩ የመረጃ ስርዓት (System) **በራሱ ጊዜ እገዳውን እንዲያነሳ** ተደርጓል።
አዲስ የቀነ-ገደብ ማሳሰቢያ
እስካሁን ያላስተሳሰሩ እና በሌሎች የሀገሪቱ ክፍሎች የሚገኙ ደንበኞች፣ የፋይዳ መታወቂያቸውን እስከ ሰኔ 30 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ በማስተሳሰር ሂሳባቸውን በቀጣይነት ማንቀሳቀስ እንዲችሉ ባንኩ በጥብቅ አሳስቧል።
የማስተሳሰሪያ አማራጮች፦
በማንኛውም የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ቅርንጫፍ በአካል በመገኘት።
በባንኩ የበይነ መረብ (Online) ማስተሳሰሪያ አማራጭ፦ 👉 https://cbefayda.cbe.com.e...
ባንኩ ደንበኞች በመጉላላታቸው ይቅርታ የጠየቀ ሲሆን፣ የደንበኞችን እርካታ እውን ለማድረግ መስራቱን እንደሚቀጥል አረጋግጧል።
#getu #cbe #commercialbankofethiopia #nationalid #faydaid #bankblockethiopia #onlineregistration #systemupdate #customersatisfaction #ሰበርዜና #ኢትዮጵያንግድባንክ #ፋይዳመታወቂያ #የባንክእገዳ #የዲጂታልኢትዮጵያ #ጌጡተመስገን #getutemesgen
5 months ago
የሴቶች ፕሪሚየር ሊግ
ኢትዮ ኤሌክትሪክ መሪነቱን ሲያጠናክር፣ ንግድ ባንክ ድሉን ቀጥሏል
#ethiopia | የ17ኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታዎች ዛሬ ሲጀምሩ፣ መሪው ኢትዮ ኤሌክትሪክ እና ተከታዩ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ተጋጣሚዎቻቸውን በማሸነፍ ነጥባቸውን አሳድገዋል።
የጨዋታዎቹ ዝርዝር ውጤት እንደሚከተለው ቀርቧል፦
⚡️ ኢትዮ ኤሌክትሪክ 3-1 ድሬዳዋ ከተማ
መሪው ኢትዮ ኤሌክትሪክ ድሬዳዋ ከተማን በመርታት የደረጃ ሰንጠረዡን አናት ይበልጥ ተቆጣጥሯል።
የኤሌክትሪክ ግቦች፦
ዳግማዊት ሰለሞን፣ ማህሌት ምትኩ እና ዙፋን ደፈርሻ።
የድሬዳዋ ግብ፦
ዝናሽ ሰለሞን።
ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 3-1 ይርጋጨፌ ቡና
ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ተከታታይ 3ኛ ድሉን በማስመዝገብ ግስጋሴውን ቀጥሏል።
የንግድ ባንክ ግቦች፦
እሙሽ ዳንኤል፣ እፀገነት ቡዙነህ እና ረድኤት አስረሳኸኝ።
የይርጋጨፌ ግብ፦
አዳነች አሰፋው።
🤝 ልደታ ክፍለ ከተማ 2-2 ቦሌ ክፍለ ከተማ
የሁለቱ ክፍለ ከተማ ቡድኖች ፍልሚያ በአቻ ውጤት ተጠናቋል።
የልደታ ግቦች፦
ሰብለወንጌል ወዳጆ እና ይታገሱ ተገኝ ወርቅ።
የቦሌ ግቦች፦
ቃልኪዳን ሸዋነህ እና ዳሳሽ ሰው አገኝ።
በሀና ታሪኩ
#የሴቶችፕሪሚየርሊግ #ኢትዮኤሌክትሪክ #ንግድባንክ #ኢትዮጵያ #እግርኳስ #getu #temesgen #getutemesgen #ጌጡ #ተመስገን #ጌጡተመስገን
ኢትዮ ኤሌክትሪክ መሪነቱን ሲያጠናክር፣ ንግድ ባንክ ድሉን ቀጥሏል
#ethiopia | የ17ኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታዎች ዛሬ ሲጀምሩ፣ መሪው ኢትዮ ኤሌክትሪክ እና ተከታዩ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ተጋጣሚዎቻቸውን በማሸነፍ ነጥባቸውን አሳድገዋል።
የጨዋታዎቹ ዝርዝር ውጤት እንደሚከተለው ቀርቧል፦
⚡️ ኢትዮ ኤሌክትሪክ 3-1 ድሬዳዋ ከተማ
መሪው ኢትዮ ኤሌክትሪክ ድሬዳዋ ከተማን በመርታት የደረጃ ሰንጠረዡን አናት ይበልጥ ተቆጣጥሯል።
የኤሌክትሪክ ግቦች፦
ዳግማዊት ሰለሞን፣ ማህሌት ምትኩ እና ዙፋን ደፈርሻ።
የድሬዳዋ ግብ፦
ዝናሽ ሰለሞን።
ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 3-1 ይርጋጨፌ ቡና
ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ተከታታይ 3ኛ ድሉን በማስመዝገብ ግስጋሴውን ቀጥሏል።
የንግድ ባንክ ግቦች፦
እሙሽ ዳንኤል፣ እፀገነት ቡዙነህ እና ረድኤት አስረሳኸኝ።
የይርጋጨፌ ግብ፦
አዳነች አሰፋው።
🤝 ልደታ ክፍለ ከተማ 2-2 ቦሌ ክፍለ ከተማ
የሁለቱ ክፍለ ከተማ ቡድኖች ፍልሚያ በአቻ ውጤት ተጠናቋል።
የልደታ ግቦች፦
ሰብለወንጌል ወዳጆ እና ይታገሱ ተገኝ ወርቅ።
የቦሌ ግቦች፦
ቃልኪዳን ሸዋነህ እና ዳሳሽ ሰው አገኝ።
በሀና ታሪኩ
#የሴቶችፕሪሚየርሊግ #ኢትዮኤሌክትሪክ #ንግድባንክ #ኢትዮጵያ #እግርኳስ #getu #temesgen #getutemesgen #ጌጡ #ተመስገን #ጌጡተመስገን
6 months ago
አቶ አቤ ሳኖ የህክምና ክትትላቸውን በተሳካ ሁኔታ አጠናቀው ወደ ስራቸው ተመለሱ
#ethiopia | የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፕሬዚደንት አቶ አቤ ሳኖ፣ በውጭ ሀገር ሲከታተሉ የነበሩትን ህክምና አጠናቅቀው በዛሬው ዕለት በይፋ ወደ ስራ ገበታቸው ተመለሱ።
ፕሬዚደንቱ ዛሬ ጠዋት በባንኩ ዋና መሥሪያ ቤት ቢሮአቸው ሲደርሱ፣ በስራ አመራር አባላት ደማቅ የ"እንኳን ደህና መጡ" አቀባበል ተደርጎላቸዋል። አቶ አቤ በአሁኑ ወቅት "በሙሉ ጤንነት" ላይ እንደሚገኙና ወደ ስራ በመመለሳቸው የተሰማቸውን ደስታ ገልጸዋል።
ከአቀባበል ሥነ-ሥርዓቱ የተሰሙ ዋና ዋና ነጥቦች፦
* የአመራሩ አንድነት፦ የባንኩ የኮርፖሬት አገልግሎቶች ኤክዝኪዩቲቭ ምክትል ፕሬዚደንት አቶ ኤፍሬም መኩሪያ፤ ፕሬዚደንቱ በሌሉበት ወቅት የባንኩ ቦርድና አመራሮች በቅንጅት በመስራት ምንም ዓይነት የሥራ ክፍተት እንዳይፈጠር ማድረጋቸውን ገልጸዋል። የአቶ አቤ መመለስም ለባንኩ ሰራተኞች "ድርብ ደስታ" መሆኑን ተናግረዋል።
* ምስጋና እና አድናቆት፦ አቶ አቤ ሳኖ በህክምና ላይ በነበሩበት ወቅት በስልክና በኢሜል መልካም ምኞታቸውን ለገለጹላቸው ባልደረቦቻቸው ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
* ያልተቋረጠ ስኬት፦ ፕሬዚደንቱ እርሳቸው በሌሉበት ወቅት ባንኩ ላስመዘገበው ስኬትና አመራሮቹ ላሳዩት ከፍተኛ የኃላፊነት ስሜት ያላቸውን አድናቆት ገልጸዋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #አቤሳኖ #የኢትዮጵያንግድባንክ #cbe #ethiopia #banking #abesano #businessnews #ethiopianeconomy
#ethiopia | የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፕሬዚደንት አቶ አቤ ሳኖ፣ በውጭ ሀገር ሲከታተሉ የነበሩትን ህክምና አጠናቅቀው በዛሬው ዕለት በይፋ ወደ ስራ ገበታቸው ተመለሱ።
ፕሬዚደንቱ ዛሬ ጠዋት በባንኩ ዋና መሥሪያ ቤት ቢሮአቸው ሲደርሱ፣ በስራ አመራር አባላት ደማቅ የ"እንኳን ደህና መጡ" አቀባበል ተደርጎላቸዋል። አቶ አቤ በአሁኑ ወቅት "በሙሉ ጤንነት" ላይ እንደሚገኙና ወደ ስራ በመመለሳቸው የተሰማቸውን ደስታ ገልጸዋል።
ከአቀባበል ሥነ-ሥርዓቱ የተሰሙ ዋና ዋና ነጥቦች፦
* የአመራሩ አንድነት፦ የባንኩ የኮርፖሬት አገልግሎቶች ኤክዝኪዩቲቭ ምክትል ፕሬዚደንት አቶ ኤፍሬም መኩሪያ፤ ፕሬዚደንቱ በሌሉበት ወቅት የባንኩ ቦርድና አመራሮች በቅንጅት በመስራት ምንም ዓይነት የሥራ ክፍተት እንዳይፈጠር ማድረጋቸውን ገልጸዋል። የአቶ አቤ መመለስም ለባንኩ ሰራተኞች "ድርብ ደስታ" መሆኑን ተናግረዋል።
* ምስጋና እና አድናቆት፦ አቶ አቤ ሳኖ በህክምና ላይ በነበሩበት ወቅት በስልክና በኢሜል መልካም ምኞታቸውን ለገለጹላቸው ባልደረቦቻቸው ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
* ያልተቋረጠ ስኬት፦ ፕሬዚደንቱ እርሳቸው በሌሉበት ወቅት ባንኩ ላስመዘገበው ስኬትና አመራሮቹ ላሳዩት ከፍተኛ የኃላፊነት ስሜት ያላቸውን አድናቆት ገልጸዋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #አቤሳኖ #የኢትዮጵያንግድባንክ #cbe #ethiopia #banking #abesano #businessnews #ethiopianeconomy
10 months ago
የጉባኤ ቤቱን እንስራ!!
መሠረቱን አንፀን የእምነት ፊታውራሪዎችን እናፍራ!!!!
በሰሜን ወሎ ራያቆቦ ወረዳ ሮቢት ከተማ ወረመኛ ደብረ ብስራት ቅዱስ ገብርኤልናአቡነ ገብረ መንፈስቅዱስ ቤተክርስቲያን የዝማሬና ቅዳሴ (ጉባኤቤት)
ክረምቱን ዝናብ እና ብርድ በጋውን ንፋስ እና ፀሃይ እየተፈራረቀ ቅኔውን ዝማሬ እና ማህሌቱን ለመቅሰም ተቸግረዋል የእናንተ በጎ ፍቃድ የእኛን ተስፋ የእኛን የነገ መዳረሻ ይወስናል እያሉ ነው!!
ውድ የኦርቶዶክስ ልጆች ከተሠጣችሁ በመስጠት የልጆቻችሁን መማሪያም ማደሪም አብጁ!!
ለበለጠ መረጃ
+251938297270
+251918501886
+251935245767
ወረመኛ ደብረ ብስራት
ቅዱስ ገብርኤል ቤ/ን
1000577647716 ንግድባንክ
0189223307 አቢሲንያ
Comments