2 days ago
የአሜሪካ መንግሥት ከአፍሪካ ቪዛ አገልግሎት መስጫ ማዕከላትን መካከል ኢትዮጵያን አልቀነሳትም
#ethiopia | የአሜሪካ መንግሥት በአፍሪካ አህጉሉአንዳ የሚሰጠውን የቪዛ አገልግሎት በከፍተኛ ደረጃ ለማሻሻል እየተዘጋጀ ነው።
በዚህ መሠረት በአፍሪካ ውስጥ የቪዛ አገልግሎት የሚሰጡ የአሜሪካ ኤምባሲዎችና ቆንስላዎች ቁጥር ከ50 ወደ 20 ብቻ ለመቀነስ ወስኗል። ይህ ለውጥ በቅርብ ጊዜያት ይጀመራል ተብሏል።
የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ ያጸደቁት ይህ አዲስ እቅድ፣ በአፍሪካ 20 ዋና የክልል ማዕከላት (Regional Hubs) በመሾም፣ ሌሎች ቦታዎችን የቪዛ ሙሉ አገልግሎት እንዳይሰጡ ለመዝጋት ያቀደ ነው።
እነዚህ የ20 ዋና ማዕከላት የትኞቹ ናቸው ፦
° አዲስ አበባ (ኢትዮጵያ) 🇪🇹
° አክራ (ጋና) 🇬🇭
° ዳካር (ሴኔጋል) 🇸🇳
° ጅቡቲ (ጅቡቲ) 🇩🇯
° ካምፓላ (ኡጋንዳ) 🇺🇬
° ኪጋሊ (ሩዋንዳ) 🇷🇼
° ኪንሻሳ (ኮንጎ) 🇨🇩
° ላጎስ (ናይጄሪያ) 🇳🇬
° ናይሮቢ (ኬንያ) 🇰🇪
° አቢጃን (አይቮሪ ኮስት) 🇨🇮
° ዳሬሰላም (ታንዛኒያ) 🇹🇿
° ሎሜ (ቶጎ) 🇹🇬
° ሉዋአንዳ (አንጎላ) 🇦🇴
° ማላቦ (ኢኳቶሪያል ጊኒ) 🇬🇶
° ሞንሮቪያ (ላይቤሪያ) 🇱🇷
° ፖርት ሉዊስ (ሞሪሸስ) 🇲🇺
° ፕራያ (ኬፕ ቨርዴ) 🇻🇪
° ያውንዴ (ካሜሩን) 🇨🇲
° ኬፕ ታውን (ደቡብ አፍሪካ) 🇿🇦
° ጆሃንስበርግ (ደቡብ አፍሪካ) 🇿🇦
ከእንግዲህ ወዲያ በእነዚህ 20 ማዕከላት ያልተካተቱ ሀገራት ዜጎች የቪዛ ቃለ መጠይቅ፣ የጣት አሻራ እና ሌሎች ሂደቶችን ለማጠናቀቅ በራሳቸው ወጪ ወደ ቅርብ ማዕከል መጓዝ ይጠበቅባቸዋል ተብሏል ያለው ቲክቫህ ነው።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#ethiopia | የአሜሪካ መንግሥት በአፍሪካ አህጉሉአንዳ የሚሰጠውን የቪዛ አገልግሎት በከፍተኛ ደረጃ ለማሻሻል እየተዘጋጀ ነው።
በዚህ መሠረት በአፍሪካ ውስጥ የቪዛ አገልግሎት የሚሰጡ የአሜሪካ ኤምባሲዎችና ቆንስላዎች ቁጥር ከ50 ወደ 20 ብቻ ለመቀነስ ወስኗል። ይህ ለውጥ በቅርብ ጊዜያት ይጀመራል ተብሏል።
የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ ያጸደቁት ይህ አዲስ እቅድ፣ በአፍሪካ 20 ዋና የክልል ማዕከላት (Regional Hubs) በመሾም፣ ሌሎች ቦታዎችን የቪዛ ሙሉ አገልግሎት እንዳይሰጡ ለመዝጋት ያቀደ ነው።
እነዚህ የ20 ዋና ማዕከላት የትኞቹ ናቸው ፦
° አዲስ አበባ (ኢትዮጵያ) 🇪🇹
° አክራ (ጋና) 🇬🇭
° ዳካር (ሴኔጋል) 🇸🇳
° ጅቡቲ (ጅቡቲ) 🇩🇯
° ካምፓላ (ኡጋንዳ) 🇺🇬
° ኪጋሊ (ሩዋንዳ) 🇷🇼
° ኪንሻሳ (ኮንጎ) 🇨🇩
° ላጎስ (ናይጄሪያ) 🇳🇬
° ናይሮቢ (ኬንያ) 🇰🇪
° አቢጃን (አይቮሪ ኮስት) 🇨🇮
° ዳሬሰላም (ታንዛኒያ) 🇹🇿
° ሎሜ (ቶጎ) 🇹🇬
° ሉዋአንዳ (አንጎላ) 🇦🇴
° ማላቦ (ኢኳቶሪያል ጊኒ) 🇬🇶
° ሞንሮቪያ (ላይቤሪያ) 🇱🇷
° ፖርት ሉዊስ (ሞሪሸስ) 🇲🇺
° ፕራያ (ኬፕ ቨርዴ) 🇻🇪
° ያውንዴ (ካሜሩን) 🇨🇲
° ኬፕ ታውን (ደቡብ አፍሪካ) 🇿🇦
° ጆሃንስበርግ (ደቡብ አፍሪካ) 🇿🇦
ከእንግዲህ ወዲያ በእነዚህ 20 ማዕከላት ያልተካተቱ ሀገራት ዜጎች የቪዛ ቃለ መጠይቅ፣ የጣት አሻራ እና ሌሎች ሂደቶችን ለማጠናቀቅ በራሳቸው ወጪ ወደ ቅርብ ማዕከል መጓዝ ይጠበቅባቸዋል ተብሏል ያለው ቲክቫህ ነው።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
21 days ago
ለዓለም ዋንጫ ተጓዦች የተጣለው የቪዛ ማስያዣ ተነሳ
#fastmereja I የዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ለ2026ቱ የዓለም ዋንጫ ወደ አሜሪካ ለሚጓዙ ደጋፊዎች ጥለውት የነበረውን የቪዛ ማስያዣ ቅድመ ሁኔታ ማንሳቱን አስታወቀ።
ከዚህ ቀደም በፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ አስተዳደር ከ50 ሀገራት የሚመጡ መንገደኞች ከ5,000 እስከ 15,000 ዶላር ተመላሽ የሚሆን ገንዘብ እንዲያስይዙ ተደንግጎ የነበረ ቢሆንም፣ አሁን ግን የውድድሩ ተጫዋቾች፣ የስፖርት አመራሮች እና የጨዋታ ትኬት ያላቸው ደጋፊዎች ይህ ክፍያ እንደማይመለከታቸው ተገልጿል።
ይህ ውሳኔ በተለይ ለዓለም ዋንጫው ማለፋቸውን ላረጋገጡና በደንቡ ተጽዕኖ ስር ለነበሩት አምስት የአፍሪካ ሀገራት (አልጄሪያ፣ ኬፕ ቨርዴ፣ አይቮሪ ኮስት፣ ሴኔጋል እና ቱንዚያ) ደጋፊዎች ትልቅ እፎይታን እንደሚፈጥር ተነግሯል። ደጋፊዎቹ ከክፍያው ነጻ ለመሆን የፊፋን የቀዳሚነት የቪዛ አሰጣጥ ሥርዓት መጠቀም እንዳለባቸው ተመልክቷል።
የ2026ቱ የዓለም ዋንጫ በዩናይትድ ስቴትስ፣ በካናዳ እና በሜክሲኮ አስተናጋጅነት እንደሚካሄድ ይታወቃል።
#fastmereja I የዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ለ2026ቱ የዓለም ዋንጫ ወደ አሜሪካ ለሚጓዙ ደጋፊዎች ጥለውት የነበረውን የቪዛ ማስያዣ ቅድመ ሁኔታ ማንሳቱን አስታወቀ።
ከዚህ ቀደም በፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ አስተዳደር ከ50 ሀገራት የሚመጡ መንገደኞች ከ5,000 እስከ 15,000 ዶላር ተመላሽ የሚሆን ገንዘብ እንዲያስይዙ ተደንግጎ የነበረ ቢሆንም፣ አሁን ግን የውድድሩ ተጫዋቾች፣ የስፖርት አመራሮች እና የጨዋታ ትኬት ያላቸው ደጋፊዎች ይህ ክፍያ እንደማይመለከታቸው ተገልጿል።
ይህ ውሳኔ በተለይ ለዓለም ዋንጫው ማለፋቸውን ላረጋገጡና በደንቡ ተጽዕኖ ስር ለነበሩት አምስት የአፍሪካ ሀገራት (አልጄሪያ፣ ኬፕ ቨርዴ፣ አይቮሪ ኮስት፣ ሴኔጋል እና ቱንዚያ) ደጋፊዎች ትልቅ እፎይታን እንደሚፈጥር ተነግሯል። ደጋፊዎቹ ከክፍያው ነጻ ለመሆን የፊፋን የቀዳሚነት የቪዛ አሰጣጥ ሥርዓት መጠቀም እንዳለባቸው ተመልክቷል።
የ2026ቱ የዓለም ዋንጫ በዩናይትድ ስቴትስ፣ በካናዳ እና በሜክሲኮ አስተናጋጅነት እንደሚካሄድ ይታወቃል።
21 days ago
የ15 ሺህ ዶላር የቪዛ ማስያዣው ቀረ
የቀጣዩን የዓለም ዋንጫ ትኬት ለገዙ ተመልካቾች የአሜሪካ መንግሥት ልዩ እፎይታ የሚሰጥ ውሳኔ አስተላለፈ።
ቀደም ሲል የቪዛ ቆይታ ጊዜያቸውን የሚያሳልፉ ሰዎችን ለመቀነስ በሚል ተጥሎ የነበረው የ15,000 ዶላር (ከ850,000 ብር በላይ) የቪዛ ማስያዣ ክፍያ፣ ትኬት በገዙ የ50 አገራት ዜጎች ላይ ተፈጻሚ እንደማይሆን የትራምፕ አስተዳደር በይፋ አስታውቋል።
ይህ ውሳኔ በተለይ ለአምስቱ የአፍሪካ አገራት (አልጄርያ፣ ኬፕ ቨርዴ፣ አይቮሪ ኮስት፣ ሴኔጋል እና ቱኒዝያ) ደጋፊዎች ትልቅ እድል የፈጠረ ሲሆን፣ ተጫዋቾችና አሠልጣኞችም ከዚህ ቀደም ከክፍያው ነፃ መደረጋቸው ይታወሳል።
ይሁን እንጂ እንደ ኢራን እና ሔይቲ ያሉ አገራት ደጋፊዎች አሁንም በውሳኔው ውስጥ ያልተካተቱ ሲሆን፣ ቱሪስቶች የአምስት ዓመት የማኅበራዊ ሚዲያ ታሪካቸውን እንዲያቀርቡ የሚጠይቀው ደንብ እንደጸና ይገኛል።
ፊፋ ከዋይት ሀውስ ጋር በመተባበር ስኬታማ ውድድር ለማካሄድ እየሰራ መሆኑን ገልጾ፣ የአሜሪካ መንግሥት ላሳየው ትብብር ምስጋናውን አቅርቧል።
አሜሪካ፣ ካናዳ እና ሜክሲኮ በጋራ በሚያስተናግዱት በዚህ ታላቅ ስፖርታዊ ኩነት ላይ ተመልካቾች የቪዛ ቆይታቸውን አክብረው ከወጡ ያስያዙት ገንዘብ (ክፍያው በሚመለከታቸው ላይ) ተመላሽ እንደሚደረግላቸው ተገልጿል።
seledadotio
seledadotio
የቀጣዩን የዓለም ዋንጫ ትኬት ለገዙ ተመልካቾች የአሜሪካ መንግሥት ልዩ እፎይታ የሚሰጥ ውሳኔ አስተላለፈ።
ቀደም ሲል የቪዛ ቆይታ ጊዜያቸውን የሚያሳልፉ ሰዎችን ለመቀነስ በሚል ተጥሎ የነበረው የ15,000 ዶላር (ከ850,000 ብር በላይ) የቪዛ ማስያዣ ክፍያ፣ ትኬት በገዙ የ50 አገራት ዜጎች ላይ ተፈጻሚ እንደማይሆን የትራምፕ አስተዳደር በይፋ አስታውቋል።
ይህ ውሳኔ በተለይ ለአምስቱ የአፍሪካ አገራት (አልጄርያ፣ ኬፕ ቨርዴ፣ አይቮሪ ኮስት፣ ሴኔጋል እና ቱኒዝያ) ደጋፊዎች ትልቅ እድል የፈጠረ ሲሆን፣ ተጫዋቾችና አሠልጣኞችም ከዚህ ቀደም ከክፍያው ነፃ መደረጋቸው ይታወሳል።
ይሁን እንጂ እንደ ኢራን እና ሔይቲ ያሉ አገራት ደጋፊዎች አሁንም በውሳኔው ውስጥ ያልተካተቱ ሲሆን፣ ቱሪስቶች የአምስት ዓመት የማኅበራዊ ሚዲያ ታሪካቸውን እንዲያቀርቡ የሚጠይቀው ደንብ እንደጸና ይገኛል።
ፊፋ ከዋይት ሀውስ ጋር በመተባበር ስኬታማ ውድድር ለማካሄድ እየሰራ መሆኑን ገልጾ፣ የአሜሪካ መንግሥት ላሳየው ትብብር ምስጋናውን አቅርቧል።
አሜሪካ፣ ካናዳ እና ሜክሲኮ በጋራ በሚያስተናግዱት በዚህ ታላቅ ስፖርታዊ ኩነት ላይ ተመልካቾች የቪዛ ቆይታቸውን አክብረው ከወጡ ያስያዙት ገንዘብ (ክፍያው በሚመለከታቸው ላይ) ተመላሽ እንደሚደረግላቸው ተገልጿል።
seledadotio
seledadotio
24 days ago
ያንጎ ግሩፕ ለ2026 የፌሎውሺፕ መርሃ ግብር ኢትዮጵያውያንን ጨምሮ የ24 ተሳታፊዎችን ዝርዝር ይፋ አደረገ
#ethiopia | ያንጎ ግሩፕ ከስድስት የአፍሪካ ሀገራት የተውጣጡና ከ600 በላይ ከሚሆኑ አመልካቾች መካከል የተመረጡ 24 የ2026 የያንጎ ፌሎውሺፕ ፕሮግራም ተሳታፊዎችን ስም ዝርዝር በይፋ አስታውቋል።
እነዚህ ተሳታፊዎች በ12 ሳምንታት የቆይታ ጊዜያቸው የቴክኒክ ክህሎታቸውን በመጠቀም በሳይንስና ቴክኖሎጂ ላይ የተመሰረቱ የፈጠራ ስራዎችን የሚያከናውኑ ሲሆን በመጨረሻም በአቢጃን በሚዘጋጅ ልዩ መድረክ ላይ ውጤታቸውን ያቀርባሉ።
ተሳታፊዎቹ ከኢትዮጵያ፣ ከኮት ዲቯር፣ ከዛምቢያ፣ ከሴኔጋል፣ ከሞዛምቢክ እና ከጋና የመጡ ናቸው።
መርሃ ግብሩ በዘንድሮው የጥናት ዓመት ተደራሽነቱን በማስፋት ከሁለት ወደ ስድስት ሀገራት ማደጉ ተገልጿል።
የዘንድሮው ትኩረትም በአርቴፊሻል ኢንተሊጀንስ ወይም በሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) ተግባራዊ አጠቃቀም ላይ ያተኮረ ነው።
በዚህም እንደ ጤና፣ የኃይል ቁጥጥር፣ የትራፊክ ማሻሻያ እና የትምህርት መፍትሄዎችን ያካተቱ የቴክኖሎጂ ውጤቶች ለዕይታ ይቀርባሉ።
ይህ የፌሎውሺፕ መርሃ ግብር በሶስት ዋና ዋና ክፍሎች የተከፈለ ሲሆን ችግር ፈቺ ጥናቶችን ማካተት፣ የምርት ልማት እና የመጨረሻ የአቀራረብ ደረጃዎችን ይይዛል።
በፕሮግራሙ ማጠቃለያ ላይ በሚከናወነው የዲሞ ደይ ዝግጅት ተሳታፊዎች ስራቸውን ለባለሙያዎች የሚያቀርቡ ሲሆን ተስፋ ላላቸው ፕሮጀክቶችም የፋይናንስ ድጋፍ ሊደረግላቸው እንደሚችል ተጠቁሟል።
የያንጎ ግሩፕ ዋና የንግድ ጉዳዮች ኃላፊ አዴኒዪ አዴባዮ እንደገለጹት ፕሮግራሙ በአካባቢው የቴክኖሎጂ እድገት ላይ የሚደረግ የረጅም ጊዜ ኢንቨስትመንት ነው።
ተቋሙ የአፍሪካን የቴክኖሎጂ ፍላጎት የሚፈቱ የፈጠራ ባለቤቶችን ለመደገፍ እና ከአንድ ሀገር በላይ ሊሰሩ የሚችሉ ምርቶች እንዲበለጽጉ ለማገዝ ፍላጎት እንዳለውም አክለዋል።
በአሁኑ ወቅት አፍሪካ ከ2.5 ሚሊዮን በላይ የሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ፣ ኢንጂነሪንግ እና ሂሳብ (STEM) ባለሙያዎች እጥረት እንዳለባት የዓለም ባንክ መረጃ ያሳያል።
በመሆኑም ይህ ፕሮግራም በተግባራዊ ስልጠና እና በባለሙያዎች ምክር የታገዘ በመሆኑ ለዘርፉ እድገት ትልቅ አስተዋጽኦ ይኖረዋል።
ቀደም ሲል የነበሩ ተሳታፊዎች በተለያዩ ማህበራዊ አገልግሎቶች ላይ ውጤታማ ስራዎችን የሰሩ ሲሆን አንዳንዶቹም የራሳቸውን የዲጂታል ምርቶችና ኩባንያዎች መመስረት መቻላቸው ተመላክቷል።
ያንጎ ግሩፕ የተለያዩ የቴክኖሎጂ ውጤቶችን ወደ እለት ተእለት አገልግሎት በመቀየር የሚታወቅ ዓለም አቀፍ ኩባንያ ነው።
ተቋሙ በትራንስፖርት፣ በማድረስ፣ በመዝናኛ እና በሌሎች ዲጂታል ዘርፎች በአፍሪካና በተለያዩ የዓለም ክፍሎች አገልግሎት በመስጠት ላይ ይገኛል።
#yangogroup #yangofellowship #technology #africatech #ai #innovation #stem #ethiopianews #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | ያንጎ ግሩፕ ከስድስት የአፍሪካ ሀገራት የተውጣጡና ከ600 በላይ ከሚሆኑ አመልካቾች መካከል የተመረጡ 24 የ2026 የያንጎ ፌሎውሺፕ ፕሮግራም ተሳታፊዎችን ስም ዝርዝር በይፋ አስታውቋል።
እነዚህ ተሳታፊዎች በ12 ሳምንታት የቆይታ ጊዜያቸው የቴክኒክ ክህሎታቸውን በመጠቀም በሳይንስና ቴክኖሎጂ ላይ የተመሰረቱ የፈጠራ ስራዎችን የሚያከናውኑ ሲሆን በመጨረሻም በአቢጃን በሚዘጋጅ ልዩ መድረክ ላይ ውጤታቸውን ያቀርባሉ።
ተሳታፊዎቹ ከኢትዮጵያ፣ ከኮት ዲቯር፣ ከዛምቢያ፣ ከሴኔጋል፣ ከሞዛምቢክ እና ከጋና የመጡ ናቸው።
መርሃ ግብሩ በዘንድሮው የጥናት ዓመት ተደራሽነቱን በማስፋት ከሁለት ወደ ስድስት ሀገራት ማደጉ ተገልጿል።
የዘንድሮው ትኩረትም በአርቴፊሻል ኢንተሊጀንስ ወይም በሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) ተግባራዊ አጠቃቀም ላይ ያተኮረ ነው።
በዚህም እንደ ጤና፣ የኃይል ቁጥጥር፣ የትራፊክ ማሻሻያ እና የትምህርት መፍትሄዎችን ያካተቱ የቴክኖሎጂ ውጤቶች ለዕይታ ይቀርባሉ።
ይህ የፌሎውሺፕ መርሃ ግብር በሶስት ዋና ዋና ክፍሎች የተከፈለ ሲሆን ችግር ፈቺ ጥናቶችን ማካተት፣ የምርት ልማት እና የመጨረሻ የአቀራረብ ደረጃዎችን ይይዛል።
በፕሮግራሙ ማጠቃለያ ላይ በሚከናወነው የዲሞ ደይ ዝግጅት ተሳታፊዎች ስራቸውን ለባለሙያዎች የሚያቀርቡ ሲሆን ተስፋ ላላቸው ፕሮጀክቶችም የፋይናንስ ድጋፍ ሊደረግላቸው እንደሚችል ተጠቁሟል።
የያንጎ ግሩፕ ዋና የንግድ ጉዳዮች ኃላፊ አዴኒዪ አዴባዮ እንደገለጹት ፕሮግራሙ በአካባቢው የቴክኖሎጂ እድገት ላይ የሚደረግ የረጅም ጊዜ ኢንቨስትመንት ነው።
ተቋሙ የአፍሪካን የቴክኖሎጂ ፍላጎት የሚፈቱ የፈጠራ ባለቤቶችን ለመደገፍ እና ከአንድ ሀገር በላይ ሊሰሩ የሚችሉ ምርቶች እንዲበለጽጉ ለማገዝ ፍላጎት እንዳለውም አክለዋል።
በአሁኑ ወቅት አፍሪካ ከ2.5 ሚሊዮን በላይ የሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ፣ ኢንጂነሪንግ እና ሂሳብ (STEM) ባለሙያዎች እጥረት እንዳለባት የዓለም ባንክ መረጃ ያሳያል።
በመሆኑም ይህ ፕሮግራም በተግባራዊ ስልጠና እና በባለሙያዎች ምክር የታገዘ በመሆኑ ለዘርፉ እድገት ትልቅ አስተዋጽኦ ይኖረዋል።
ቀደም ሲል የነበሩ ተሳታፊዎች በተለያዩ ማህበራዊ አገልግሎቶች ላይ ውጤታማ ስራዎችን የሰሩ ሲሆን አንዳንዶቹም የራሳቸውን የዲጂታል ምርቶችና ኩባንያዎች መመስረት መቻላቸው ተመላክቷል።
ያንጎ ግሩፕ የተለያዩ የቴክኖሎጂ ውጤቶችን ወደ እለት ተእለት አገልግሎት በመቀየር የሚታወቅ ዓለም አቀፍ ኩባንያ ነው።
ተቋሙ በትራንስፖርት፣ በማድረስ፣ በመዝናኛ እና በሌሎች ዲጂታል ዘርፎች በአፍሪካና በተለያዩ የዓለም ክፍሎች አገልግሎት በመስጠት ላይ ይገኛል።
#yangogroup #yangofellowship #technology #africatech #ai #innovation #stem #ethiopianews #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
24 days ago
ያንጎ ግሩፕ፣ ከ6 የአፍሪካ ሀገራት ውስጥ የተመረጡ የ2026 የያንጎ ፌሎውሺፕ ፕሮግራም ተሳታፊዎችን ይፋ አደረገ!
...
አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ ፤
ያንጎ ግሩፕ፣ ከ6 የአፍሪካ ሀገራት እና ከ600 አመልካቾች ውስጥ የተመረጡ 24 የ2026 የያንጎ ፌሎውሺፕ ፕሮግራም ተሳታፊዎችን ይፋ አደረገ! የተመረጡት ተሣታፊዎች፣ በ12 ሳምንታት ውስጥ የሳይንስና ቴክኖሎጂ መሠረት ያላቸው ፕሮጀክቶችን የቴክኒክ ክሂላቸውን በመጠቀም የሚያዘጋጁ ሲሆን በመጨረሻ በአቢጃን በሚካሄደው ልዩ ዝግጅት ላይ ሥራዎቻቸውን ያቀርባሉ።
የተመረጡት ተሳታፊዎች ከኮት ዲቯር፣ ዛምቢያ፣ ኢትዮጵያ፣ ሴኔጋል፣ ሞዛምቢክ እና ጋና የመጡ ሲሆን፣ ፕሮግራሙ ተሣታፊዎቹን በያዝነው የሥራ ዓመት ከ2 ሀገራት ወደ6 በማሳደግ ተደራሽነቱ መጨመሩን አስመስክሯል፡፡
የዘንድሮው ፕሮግራም በአርቴፊሻል ኢንተሊጀንስ (AI) ተግባራዊ አጠቃቀም ላይ ያተኩራል። ተሳታፊዎችም እንደ የጤና ዕውቀት ማበልጸጊያ መሣሪያዎች፣ የኃይል ክትትል ሥርዓቶች፣ የትራፊክ ማሻሻያ ሞዴሎች እና በአካባቢ ቋንቋዎች ላይ የተመረኮዙ የትምህርት መፍትሔዎችን ገንብተው እንደሚያሳዩ ይጠበቃል።
ፌሎውሺፑ በሦስት ደረጃዎች የተዋቀረ ነው፡፡ እነሱም፡- ዘላቂ መፍትሔ የሚያስፈልጋቸው ጉዳዮችን መለየት እና የገበያ ትንተና፣ የምርት ልማትና ዕድገት እና የመጨረሻ አቀራረብ። ፕሮግራሙ በ“ዴሞ ደይ” ወይም ተሣታፊዎች የተዘጋጁበትን ካቀረቡ በኋላ ይደመደማል፡፡ በዚህ ቀን፣ ቡድኖች ፕሮጀክቶቻቸውን ለኢንዱስትሪ ባለሙያዎች እና አጋሮች የሚያቀርቡ ሲሆን ሥራቸው ተስፋ እንዳለው ከታመነበት፣ የሥራ ማስጀመሪያ ፋይናንስ ድጋፍ (seed funding) ሊያገኙ ይችላሉ።
“የንጎ ፌሎውሺፕ ፕሮግራም፣ በአካባቢያዊ የቴክኖሎጂ ሥነምኅዳር ላይ ያቀድነው የረጅም ጊዜ ኢንቨስትመንታችን አካል ነው።” ያሉት የያንጎ ግሩፕ ዋና የንግድ ጉዳዮች ኃላፊ አዴኒዪ አዴባዮ፣ አክለውም “በቴክኖሎጂው ዘርፍ ላይ በመሰማራት ላይ ያሉ ባለተሰጥኦ ተሳታፊዎችን በመደገፍ እና በተለያዩ ገበያዎች መካከል የሥራ ትብብርን በመፍጠር፣ በአፍሪካ ገበያዎች ያሉ የቴክኖሎጂ ፍላጎቶችን የሚፈቱ የዘላቂ መፍትሔዎች ልማት ላይ ለመሳተፍ እንፈልጋለን፡፡ ጎን ለጎንም፣ አዳዲስ ሐሳብ አመንጪዎች ከአንድ ሀገር በላይ ሊሠሩ የሚችሉ ምርቶችን እንዲገነቡ እና እንዲያሳድጉ የመርዳት ከፍተኛ ፍላጎት አለን።” ሲሉ ተናግረዋል፡፡
እንደ ዓለም ባንክ ገለፃ፣ አፍሪካ ከ2.5 ሚሊዮን በላይ የሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ፣ ኢንጂነሪንግ እና ሒሳብ (STEM) ባለሙያዎች እጥረት አጋጥሟታል። በመሆኑም፣ ፕሮግራሙ በባለሙያዎች ምክር እና በተግባራዊ የፕሮጀክት ሥልጠና መሠረትነት ላይ ተመርኩዞ ተሳታፊዎችን በተግባር ወደቴክኖሎጂና ዕውቀት ልምምድ በማቅረብ፣ ወደ ቴክኖሎጂ ሙያዎች የሚያመሩትን የዕውቀት መንገዶች በሙሉ ማጠናከር ይፈልጋል።
በቀደሙት ፕሮግራሞች እና ልምድ ልውውጦች ውስጥ፣ ተሳታፊዎች በጤና፣ በትምህርት እና በምህንድስና መስኮች የተለያዩ መፍትሔዎችን አበርክተዋል። አንዳንድ የፕሮግራሙ ተመራቂዎች በአጋር ድርጅቶች ውስጥ ቀጣይነት ያላቸውን የልምምድ ሥራዎች (internships) ያገኙ ሲሆን ሌሎች ደግሞ ማኅበረሰብ ለሚጠቅሙ ፕሮጀክቶቻቸው እውን ማድረግ የሚያስችል የገንዘብ ድጋፍ ተቀብለዋል። የአልሙናይ አባላትም ከፌሎውሺፑ በኋላ አዳዲስና ጀማሪ ኩባንያዎችን፣ ዲጂታል ምርቶችን እና ለትርፍ ያልተቋቋሙ ማኅበረሰብ ተኮር ፕሮጀክቶችን በመጀመር ሥራቸውን ቀጥለዋል።
- - -
ስለያንጎ ግሩፕ
ያንጎ ግሩፕ፣ ዓለም አቀፍ የቴክኖሎጂ ኩባንያ ሲሆን በዓለም አቀፍ ደረጃ ያሉ ዘመን አፈራሽ ቴክኖሎጂዎችን ወደ ዕለታዊና ኑሮን የሚያቀሉ አገልግሎቶች በመቀየር ማኅበረሰቦችን የሚያገለግል ተቋም ነው። ለፈጠራ ባለው የማያወላውል ቁርጠኝነት፣ ከዓለም ዙሪያ መሪ ቴክኖሎጂዎችን ወደተለያዩ የዓለም ክፍሎች ያለምንም እንከን ወደ የተቀናጀ የዕለት ተዕለት አገልግሎቶች ይቀይራል፤ በየጊዜውም ያዘምናል፡፡
የያንጎ ግሩፕ፣ የትራንስፖርት፣ የማድረስ፣ የፉድቴክ፣ የመዝናኛ እና ሌሎች ዲጂታል አገልግሎቶቹን በአፍሪካ ውስጥ ባሉ ከ30 በላይ ሀገራት፣ በላቲን አሜሪካ፣ በአውሮፓ፣ በመካከለኛው ምሥራቅ፣ በደቡብ እስያ እና ሌሎች የዓለም ሀገራት ውስጥ ይሰጣል።
ለተጨማሪ መረጃ: pryango.com. ላይ ይጎብኙን፡፡
...
አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ ፤
ያንጎ ግሩፕ፣ ከ6 የአፍሪካ ሀገራት እና ከ600 አመልካቾች ውስጥ የተመረጡ 24 የ2026 የያንጎ ፌሎውሺፕ ፕሮግራም ተሳታፊዎችን ይፋ አደረገ! የተመረጡት ተሣታፊዎች፣ በ12 ሳምንታት ውስጥ የሳይንስና ቴክኖሎጂ መሠረት ያላቸው ፕሮጀክቶችን የቴክኒክ ክሂላቸውን በመጠቀም የሚያዘጋጁ ሲሆን በመጨረሻ በአቢጃን በሚካሄደው ልዩ ዝግጅት ላይ ሥራዎቻቸውን ያቀርባሉ።
የተመረጡት ተሳታፊዎች ከኮት ዲቯር፣ ዛምቢያ፣ ኢትዮጵያ፣ ሴኔጋል፣ ሞዛምቢክ እና ጋና የመጡ ሲሆን፣ ፕሮግራሙ ተሣታፊዎቹን በያዝነው የሥራ ዓመት ከ2 ሀገራት ወደ6 በማሳደግ ተደራሽነቱ መጨመሩን አስመስክሯል፡፡
የዘንድሮው ፕሮግራም በአርቴፊሻል ኢንተሊጀንስ (AI) ተግባራዊ አጠቃቀም ላይ ያተኩራል። ተሳታፊዎችም እንደ የጤና ዕውቀት ማበልጸጊያ መሣሪያዎች፣ የኃይል ክትትል ሥርዓቶች፣ የትራፊክ ማሻሻያ ሞዴሎች እና በአካባቢ ቋንቋዎች ላይ የተመረኮዙ የትምህርት መፍትሔዎችን ገንብተው እንደሚያሳዩ ይጠበቃል።
ፌሎውሺፑ በሦስት ደረጃዎች የተዋቀረ ነው፡፡ እነሱም፡- ዘላቂ መፍትሔ የሚያስፈልጋቸው ጉዳዮችን መለየት እና የገበያ ትንተና፣ የምርት ልማትና ዕድገት እና የመጨረሻ አቀራረብ። ፕሮግራሙ በ“ዴሞ ደይ” ወይም ተሣታፊዎች የተዘጋጁበትን ካቀረቡ በኋላ ይደመደማል፡፡ በዚህ ቀን፣ ቡድኖች ፕሮጀክቶቻቸውን ለኢንዱስትሪ ባለሙያዎች እና አጋሮች የሚያቀርቡ ሲሆን ሥራቸው ተስፋ እንዳለው ከታመነበት፣ የሥራ ማስጀመሪያ ፋይናንስ ድጋፍ (seed funding) ሊያገኙ ይችላሉ።
“የንጎ ፌሎውሺፕ ፕሮግራም፣ በአካባቢያዊ የቴክኖሎጂ ሥነምኅዳር ላይ ያቀድነው የረጅም ጊዜ ኢንቨስትመንታችን አካል ነው።” ያሉት የያንጎ ግሩፕ ዋና የንግድ ጉዳዮች ኃላፊ አዴኒዪ አዴባዮ፣ አክለውም “በቴክኖሎጂው ዘርፍ ላይ በመሰማራት ላይ ያሉ ባለተሰጥኦ ተሳታፊዎችን በመደገፍ እና በተለያዩ ገበያዎች መካከል የሥራ ትብብርን በመፍጠር፣ በአፍሪካ ገበያዎች ያሉ የቴክኖሎጂ ፍላጎቶችን የሚፈቱ የዘላቂ መፍትሔዎች ልማት ላይ ለመሳተፍ እንፈልጋለን፡፡ ጎን ለጎንም፣ አዳዲስ ሐሳብ አመንጪዎች ከአንድ ሀገር በላይ ሊሠሩ የሚችሉ ምርቶችን እንዲገነቡ እና እንዲያሳድጉ የመርዳት ከፍተኛ ፍላጎት አለን።” ሲሉ ተናግረዋል፡፡
እንደ ዓለም ባንክ ገለፃ፣ አፍሪካ ከ2.5 ሚሊዮን በላይ የሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ፣ ኢንጂነሪንግ እና ሒሳብ (STEM) ባለሙያዎች እጥረት አጋጥሟታል። በመሆኑም፣ ፕሮግራሙ በባለሙያዎች ምክር እና በተግባራዊ የፕሮጀክት ሥልጠና መሠረትነት ላይ ተመርኩዞ ተሳታፊዎችን በተግባር ወደቴክኖሎጂና ዕውቀት ልምምድ በማቅረብ፣ ወደ ቴክኖሎጂ ሙያዎች የሚያመሩትን የዕውቀት መንገዶች በሙሉ ማጠናከር ይፈልጋል።
በቀደሙት ፕሮግራሞች እና ልምድ ልውውጦች ውስጥ፣ ተሳታፊዎች በጤና፣ በትምህርት እና በምህንድስና መስኮች የተለያዩ መፍትሔዎችን አበርክተዋል። አንዳንድ የፕሮግራሙ ተመራቂዎች በአጋር ድርጅቶች ውስጥ ቀጣይነት ያላቸውን የልምምድ ሥራዎች (internships) ያገኙ ሲሆን ሌሎች ደግሞ ማኅበረሰብ ለሚጠቅሙ ፕሮጀክቶቻቸው እውን ማድረግ የሚያስችል የገንዘብ ድጋፍ ተቀብለዋል። የአልሙናይ አባላትም ከፌሎውሺፑ በኋላ አዳዲስና ጀማሪ ኩባንያዎችን፣ ዲጂታል ምርቶችን እና ለትርፍ ያልተቋቋሙ ማኅበረሰብ ተኮር ፕሮጀክቶችን በመጀመር ሥራቸውን ቀጥለዋል።
- - -
ስለያንጎ ግሩፕ
ያንጎ ግሩፕ፣ ዓለም አቀፍ የቴክኖሎጂ ኩባንያ ሲሆን በዓለም አቀፍ ደረጃ ያሉ ዘመን አፈራሽ ቴክኖሎጂዎችን ወደ ዕለታዊና ኑሮን የሚያቀሉ አገልግሎቶች በመቀየር ማኅበረሰቦችን የሚያገለግል ተቋም ነው። ለፈጠራ ባለው የማያወላውል ቁርጠኝነት፣ ከዓለም ዙሪያ መሪ ቴክኖሎጂዎችን ወደተለያዩ የዓለም ክፍሎች ያለምንም እንከን ወደ የተቀናጀ የዕለት ተዕለት አገልግሎቶች ይቀይራል፤ በየጊዜውም ያዘምናል፡፡
የያንጎ ግሩፕ፣ የትራንስፖርት፣ የማድረስ፣ የፉድቴክ፣ የመዝናኛ እና ሌሎች ዲጂታል አገልግሎቶቹን በአፍሪካ ውስጥ ባሉ ከ30 በላይ ሀገራት፣ በላቲን አሜሪካ፣ በአውሮፓ፣ በመካከለኛው ምሥራቅ፣ በደቡብ እስያ እና ሌሎች የዓለም ሀገራት ውስጥ ይሰጣል።
ለተጨማሪ መረጃ: pryango.com. ላይ ይጎብኙን፡፡
2 months ago
አሰልጣኝ አሊዮ ሲሴ ከሊቢያ ብሔራዊ ቡድን ጋር መለያየታቸውን ገለጹ
#ethiopia | የቀድሞው የሴኔጋል ብሔራዊ ቡድን ስኬታማ አሰልጣኝ አሊዮ ሲሴ፣ በሊቢያ ብሔራዊ ቡድን የነበራቸውን የአንድ ዓመት ቆይታ በይፋ ማጠናቀቃቸው ታውቋል።
ባለፉት 12 ወራት የሊቢያን "የሜዲትራኒያን ፈረሰኞች" ሲመሩ የቆዩት ሲሴ፣ ቡድኑን በአስር ጨዋታዎች ላይ መርተዋል።
አሊዮ ሲሴ ከሊቢያ ጋር መለያየታቸውን ተከትሎ፣ ስማቸው ከሌላኛው የአፍሪካ ግዙፍ ተገዳዳሪ ጋና (ጥቁር ከዋክብት) ጋር በስፋት እየተያያዘ ይገኛል።
ሲሴ ሴኔጋልን ለረጅም ዓመታት በመምራትና የአፍሪካ ዋንጫን በማንሳት የነበራቸው ልምድ፣ ለጋና ብሔራዊ ቡድን ትልቅ ግብዓት ሊሆን ይችላል ተብሎ ይጠበቃል።
አሊዮ ሲሴ በተለይ በሴኔጋል ብሔራዊ ቡድን ለ9 ዓመታት በቆዩበት ወቅት ለሀገራቸው የመጀመሪያውን የአፍሪካ ዋንጫ በማምጣት ትልቅ ታሪክ የሰሩ ድንቅ አሰልጣኝ መሆናቸው ይታወሳል።
አሁን ደግሞ አዲስ ፈተና ፍለጋ ወደ ጋና የሚያደርጉት ጉዞ እውን ይሆን እንደሆን ወደፊት የሚታይ ይሆናል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #alioucisse #libyafootball #ghanablackstars #africanfootball #soccernews #senegal #footballcoach
#ethiopia | የቀድሞው የሴኔጋል ብሔራዊ ቡድን ስኬታማ አሰልጣኝ አሊዮ ሲሴ፣ በሊቢያ ብሔራዊ ቡድን የነበራቸውን የአንድ ዓመት ቆይታ በይፋ ማጠናቀቃቸው ታውቋል።
ባለፉት 12 ወራት የሊቢያን "የሜዲትራኒያን ፈረሰኞች" ሲመሩ የቆዩት ሲሴ፣ ቡድኑን በአስር ጨዋታዎች ላይ መርተዋል።
አሊዮ ሲሴ ከሊቢያ ጋር መለያየታቸውን ተከትሎ፣ ስማቸው ከሌላኛው የአፍሪካ ግዙፍ ተገዳዳሪ ጋና (ጥቁር ከዋክብት) ጋር በስፋት እየተያያዘ ይገኛል።
ሲሴ ሴኔጋልን ለረጅም ዓመታት በመምራትና የአፍሪካ ዋንጫን በማንሳት የነበራቸው ልምድ፣ ለጋና ብሔራዊ ቡድን ትልቅ ግብዓት ሊሆን ይችላል ተብሎ ይጠበቃል።
አሊዮ ሲሴ በተለይ በሴኔጋል ብሔራዊ ቡድን ለ9 ዓመታት በቆዩበት ወቅት ለሀገራቸው የመጀመሪያውን የአፍሪካ ዋንጫ በማምጣት ትልቅ ታሪክ የሰሩ ድንቅ አሰልጣኝ መሆናቸው ይታወሳል።
አሁን ደግሞ አዲስ ፈተና ፍለጋ ወደ ጋና የሚያደርጉት ጉዞ እውን ይሆን እንደሆን ወደፊት የሚታይ ይሆናል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #alioucisse #libyafootball #ghanablackstars #africanfootball #soccernews #senegal #footballcoach
2 months ago
ሴኔጋል ከወዳጅነት ጨዋታዎች የ3.3 ሚሊዮን ዶላር ገቢ ማግኘቷ ተገለጸ
#ethiopia | የሴኔጋል እግር ኳስ ፌዴሬሽን በመጋቢት ወር ካደረጋቸው ዓለም አቀፍ የወዳጅነት ጨዋታዎች ከፍተኛ የገንዘብ ገቢ ማግኘቱን ይፋ አደረገ። ፌዴሬሽኑ ከፔሩ እና ጋምቢያ ብሄራዊ ቡድኖች ጋር ካደረጋቸው ጨዋታዎች በአጠቃላይ ከ3.3 ሚሊዮን ዶላር በላይ ገቢ መሰብሰቡን አስታውቋል።
የፌዴሬሽኑ ፕሬዝዳንት አብዱላይ ፎል እንደገለጹት፣ ይህ ከፍተኛ ገቢ የተገኘው በዋናነት ከቲኬት ሽያጭ ሲሆን በአንድ ጨዋታ ብቻ እስከ 1.6 ሚሊዮን ዶላር የሚጠጋ ገቢ መገኘቱ ተመዝግቧል። ይህም ለአገሪቱ እግር ኳስ እድገት ትልቅ አቅም እንደሚሆን ተገልጿል።
የሴኔጋል እና ሞሮኮ ጨዋታ አወዛጋቢ ሁኔታ
ከዚሁ ጋር በተያያዘ በሴኔጋል እና ሞሮኮ መካከል ተካሂዶ ስለነበረው ጨዋታ የዕለቱ ዳኛ ያቀረቡት ሪፖርት ይፋ ሆኗል። በሪፖርቱ መሰረት፦
* ጨዋታው በ97ኛው ደቂቃ ላይ ለጊዜው ተቋርጦ ከ12 ደቂቃ በኋላ ተመልሶ ተጀምሯል።
* በሁለቱም ቡድኖች በኩል ጨዋታውን አቋርጦ የወጣ ብሄራዊ ቡድን አለመኖሩን የዳኛው ሪፖርት በግልጽ ያሳያል።
* ይህ የዳኛው ሪፖርት ቢወጣም፣ የካፍ (CAF) ውሳኔ አሁንም በስፖርቱ ቤተሰብ ዘንድ አነጋጋሪነቱ ቀጥሏል።
የፓትሪስ ሞትሴፔ የሴኔጋል ጉብኝት
የካፍ ፕሬዝዳንት ፓትሪስ ሞትሴፔ በቅርቡ ወደ ሴኔጋል በማምራት ከከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት ጋር ውይይት እንደሚያደርጉ ተገልጿል። የጉብኝቱ ዋና ዓላማዎች፦
የካፍ ይግባኝ ኮሚቴ የ2025ቱን የአፍሪካ ዋንጫ ለሞሮኮ ለመስጠት መወሰኑን ተከትሎ የተፈጠረውን ውጥረት ለማርገብ።
በካፍ እና በአባል አገራት መካከል ያለውን ግንኙነት በማደስ፣ በአፍሪካ እግር ኳስ ውስጥ አንድነትን እና ተቀባይነትን ወደነበረበት ለመመለስ።
ጉብኝቱ በአፍሪካ እግር ኳስ አስተዳደር ላይ የተፈጠሩ አለመግባባቶችን ለመፍታት ትልቅ ሚና ይኖረዋል ተብሎ ይጠበቃል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #senegal #caf #patricemotsepe #morocco #africanfootball #footballnews #senegalfootball
#ethiopia | የሴኔጋል እግር ኳስ ፌዴሬሽን በመጋቢት ወር ካደረጋቸው ዓለም አቀፍ የወዳጅነት ጨዋታዎች ከፍተኛ የገንዘብ ገቢ ማግኘቱን ይፋ አደረገ። ፌዴሬሽኑ ከፔሩ እና ጋምቢያ ብሄራዊ ቡድኖች ጋር ካደረጋቸው ጨዋታዎች በአጠቃላይ ከ3.3 ሚሊዮን ዶላር በላይ ገቢ መሰብሰቡን አስታውቋል።
የፌዴሬሽኑ ፕሬዝዳንት አብዱላይ ፎል እንደገለጹት፣ ይህ ከፍተኛ ገቢ የተገኘው በዋናነት ከቲኬት ሽያጭ ሲሆን በአንድ ጨዋታ ብቻ እስከ 1.6 ሚሊዮን ዶላር የሚጠጋ ገቢ መገኘቱ ተመዝግቧል። ይህም ለአገሪቱ እግር ኳስ እድገት ትልቅ አቅም እንደሚሆን ተገልጿል።
የሴኔጋል እና ሞሮኮ ጨዋታ አወዛጋቢ ሁኔታ
ከዚሁ ጋር በተያያዘ በሴኔጋል እና ሞሮኮ መካከል ተካሂዶ ስለነበረው ጨዋታ የዕለቱ ዳኛ ያቀረቡት ሪፖርት ይፋ ሆኗል። በሪፖርቱ መሰረት፦
* ጨዋታው በ97ኛው ደቂቃ ላይ ለጊዜው ተቋርጦ ከ12 ደቂቃ በኋላ ተመልሶ ተጀምሯል።
* በሁለቱም ቡድኖች በኩል ጨዋታውን አቋርጦ የወጣ ብሄራዊ ቡድን አለመኖሩን የዳኛው ሪፖርት በግልጽ ያሳያል።
* ይህ የዳኛው ሪፖርት ቢወጣም፣ የካፍ (CAF) ውሳኔ አሁንም በስፖርቱ ቤተሰብ ዘንድ አነጋጋሪነቱ ቀጥሏል።
የፓትሪስ ሞትሴፔ የሴኔጋል ጉብኝት
የካፍ ፕሬዝዳንት ፓትሪስ ሞትሴፔ በቅርቡ ወደ ሴኔጋል በማምራት ከከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት ጋር ውይይት እንደሚያደርጉ ተገልጿል። የጉብኝቱ ዋና ዓላማዎች፦
የካፍ ይግባኝ ኮሚቴ የ2025ቱን የአፍሪካ ዋንጫ ለሞሮኮ ለመስጠት መወሰኑን ተከትሎ የተፈጠረውን ውጥረት ለማርገብ።
በካፍ እና በአባል አገራት መካከል ያለውን ግንኙነት በማደስ፣ በአፍሪካ እግር ኳስ ውስጥ አንድነትን እና ተቀባይነትን ወደነበረበት ለመመለስ።
ጉብኝቱ በአፍሪካ እግር ኳስ አስተዳደር ላይ የተፈጠሩ አለመግባባቶችን ለመፍታት ትልቅ ሚና ይኖረዋል ተብሎ ይጠበቃል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #senegal #caf #patricemotsepe #morocco #africanfootball #footballnews #senegalfootball
2 months ago
በነዳጅ ዋጋ ንረት ሳቢያ የሴኔጋል መንግሥት በባለስልጣናት ላይ ጥብቅ የጉዞ እገዳ ጣለ
#ethiopia | በመካከለኛው ምሥራቅ የተቀሰቀሰውን ጦርነት ተከትሎ በዓለም አቀፍ ደረጃ የተከሰተውን ከፍተኛ የነዳጅ ዋጋ ንረት ለማቋቋም፣ የሴኔጋል መንግሥት በከፍተኛ ባለስልጣናቱ ላይ የውጭ አገር የጉዞ እገዳ መጣሉን አስታወቀ።
የሀገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ዑስማን ሶንኮ በቀጣይ ጊዜያት ሀገሪቱን "እጅግ ፈታኝ" የሆኑ ሁኔታዎች ሊገጥሟት እንደሚችል ጠንከር ያለ ማሳሰቢያ ሰጥተዋል። ይህንንም ተከትሎ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ራሳቸው ለሥራ ጉዳይ ወደ ኒጀር፣ ስፔን እና ፈረንሳይ ሊያደርጉት የነበረውን ጉዞ በመሰረዝ አርአያነት ያለው እርምጃ ወስደዋል።
አዲሱ የመንግሥት መመሪያ ከሚኒስትሮች ጀምሮ እስከ ተለያዩ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎችን የሚያጠቃልል ሲሆን፣ ባለስልጣናቱ ከሚመሩት ተቋም ዋና ዓላማ ጋር ቀጥተኛና ወሳኝ ግንኙነት የሌላቸውን ማናቸውንም የውጭ ሀገር ጉዞዎች እንዳያደርጉ በይፋ ታግደዋል።
የዓለም አቀፉ የነዳጅ ገበያ አለመረጋጋት በሴኔጋል ኢኮኖሚ ላይ ከባድ ጫና እያሳደረ ይገኛል። መንግሥት የዘንድሮውን ዓመታዊ በጀት ሲያቅድ የአንድ በርሜል ድፍድፍ ነዳጅ ዋጋ 62 ዶላር ይሆናል በሚል ስሌት ላይ ተመሥርቶ የነበረ ቢሆንም፣ በአሁኑ ወቅት የብሬንት ድፍድፍ ነዳጅ ዋጋ በከፍተኛ ፍጥነት አሻቅቦ 115 ዶላር መድረሱ ለሀገሪቱ በጀት አፈጻጸም ትልቅ ፈተና ደቅኗል።
የገጠመውን የነዳጅ ዋጋ ንረትና የኢኮኖሚ ጫና በተሻለ ሁኔታ ለመምራት የሚያስችሉ ተጨማሪና ዝርዝር የመንግሥት መመሪያዎች በሚቀጥለው ሳምንት ይፋ እንደሚደረጉ ተገልጿል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ሴኔጋል #የነዳጅ_ዋጋ #ዓለም_አቀፍ_ዜና #ዑስማን_ሶንኮ #ኢኮኖሚ #senegal #africanews
#ethiopia | በመካከለኛው ምሥራቅ የተቀሰቀሰውን ጦርነት ተከትሎ በዓለም አቀፍ ደረጃ የተከሰተውን ከፍተኛ የነዳጅ ዋጋ ንረት ለማቋቋም፣ የሴኔጋል መንግሥት በከፍተኛ ባለስልጣናቱ ላይ የውጭ አገር የጉዞ እገዳ መጣሉን አስታወቀ።
የሀገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ዑስማን ሶንኮ በቀጣይ ጊዜያት ሀገሪቱን "እጅግ ፈታኝ" የሆኑ ሁኔታዎች ሊገጥሟት እንደሚችል ጠንከር ያለ ማሳሰቢያ ሰጥተዋል። ይህንንም ተከትሎ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ራሳቸው ለሥራ ጉዳይ ወደ ኒጀር፣ ስፔን እና ፈረንሳይ ሊያደርጉት የነበረውን ጉዞ በመሰረዝ አርአያነት ያለው እርምጃ ወስደዋል።
አዲሱ የመንግሥት መመሪያ ከሚኒስትሮች ጀምሮ እስከ ተለያዩ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎችን የሚያጠቃልል ሲሆን፣ ባለስልጣናቱ ከሚመሩት ተቋም ዋና ዓላማ ጋር ቀጥተኛና ወሳኝ ግንኙነት የሌላቸውን ማናቸውንም የውጭ ሀገር ጉዞዎች እንዳያደርጉ በይፋ ታግደዋል።
የዓለም አቀፉ የነዳጅ ገበያ አለመረጋጋት በሴኔጋል ኢኮኖሚ ላይ ከባድ ጫና እያሳደረ ይገኛል። መንግሥት የዘንድሮውን ዓመታዊ በጀት ሲያቅድ የአንድ በርሜል ድፍድፍ ነዳጅ ዋጋ 62 ዶላር ይሆናል በሚል ስሌት ላይ ተመሥርቶ የነበረ ቢሆንም፣ በአሁኑ ወቅት የብሬንት ድፍድፍ ነዳጅ ዋጋ በከፍተኛ ፍጥነት አሻቅቦ 115 ዶላር መድረሱ ለሀገሪቱ በጀት አፈጻጸም ትልቅ ፈተና ደቅኗል።
የገጠመውን የነዳጅ ዋጋ ንረትና የኢኮኖሚ ጫና በተሻለ ሁኔታ ለመምራት የሚያስችሉ ተጨማሪና ዝርዝር የመንግሥት መመሪያዎች በሚቀጥለው ሳምንት ይፋ እንደሚደረጉ ተገልጿል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ሴኔጋል #የነዳጅ_ዋጋ #ዓለም_አቀፍ_ዜና #ዑስማን_ሶንኮ #ኢኮኖሚ #senegal #africanews
Sponsored by
Surafel
2 months ago
የሴኔጋል መንግስት በግብረ ሰዶማዊነት ላይ ጠንካራ እርምጃ የሚወስድ አዲስ ህግ አፀደቀ።
የሴኔጋል ፕሬዝዳንት ባሲሩ ዲዮማዬ ፋዬ በሀገሪቱ ግብረ ሰዶማውያንን በከፍተኛ ሁኔታ የሚቀጣ አዲስ ህግ በፊርማቸው አፅድቀዋል።
ይህ አዲስ ህግ ቀደም ሲል በግብረ ሰዶማዊነት ድርጊት ላይ ተጥሎ የነበረውን ከፍተኛ የእስር ቅጣት ወደ 10 ዓመት ከፍ አድርጎታል።
" ከተፈጥሮ ውጪ የሆኑ ድርጊቶች " ተብለው የተመደቡ የተመሳሳይ ፆታ ግንኙነቶች ላይ የሚጣለው ቅጣት ከነበረበት 1-5 ዓመት ወደ 5-10 ዓመት ከፍ እንዲል ተደርጓል።
አዲሱ ህግ ከእስር በተጨማሪ ከ2 ሚሊዮን እስከ 10 ሚሊዮን የሴኔጋል ፍራንክ ($3,500 - $17,600) የሚደርስ ከፍተኛ የገንዘብ መቀጮ ደንግጓል። ይህም ቀደም ሲል ከነበረው (1.5 ሚሊዮን ፍራንክ) እጅግ የላቀ ነው።
ግብረ ሰዶማዊነትን የሚያስተዋውቁ ወይም የገንዘብ ድጋፍ የሚያደርጉ ግለሰቦች ከ3 እስከ 7 ዓመት በሚደርስ እስራት እንዲቀጡ ህጉ ይፈቅዳል።
አፀያፊ የተባለውን ይህን ድርጊት የሚያበረታታ ማንኛውም ድርጊት እንደ ወንጀል እንዲታይ ተደርጓል።
ህጉ ያለምንም ማስረጃ ሌላውን ሰው በግብረ ሰዶማዊነት ወንጀል የሚከስ ማንኛውንም አካል በወንጀል እንደሚቀጣ አካቷል።
ይህ ጠንካራ ህግ ፕሬዝዳንት ባሲሩ ዲዮማዬ ፋዬ እና የሀገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ኡስማን ሶንኮ በምርጫ ወቅት ለህዝባቸው የገቡትን ቃል የፈጸሙበት ነው ተብሏል።
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብአዊ መብቶች ከፍተኛ ኮሚሽነር ቮልከር ቱርክ ውሳኔውን " እጅግ አሳሳቢ " ሲሉ የገለጹት ሲሆን ህጉ ሰብአዊ መብቶችን የሚጥስ መሆኑን ተናግረዋል።
በተቃራኒው በሴኔጋል የሚገኙ የሃይማኖት ተቋማት እና ማህበራት ግብረ ሰዶማዊነት "የምዕራባውያን ባህል መጫኛ መሳሪያ ነው" በሚል ጠንካራ ቅጣት እንዲጣል ሲወተውቱ ቆይተዋል ተብሏል።
ከባለፈው የካቲት ወር ጀምሮ በሴኔጋል በርካታ ሰዎች በግብረ ሰዶማዊነት ተጠርጥረው በቁጥጥር ስር ውለዋል።
አዲሱ ህግ ተጠርጣሪዎቹ ላይ የሚጣለውን ቅጣት የበለጠ በማክበድ በሀገሪቱ ያለውን ጥብቅ ቁጥጥር የሚያጠናክር ነው።
በተለይም ድርጊቱ የተፈጸመው ለአካለ መጠን ባልደረሱ ህፃናት ላይ ከሆነ ከፍተኛው ቅጣት እንደሚተገበር ህጉ ይገልጻል።
tikvahethiopia
የሴኔጋል ፕሬዝዳንት ባሲሩ ዲዮማዬ ፋዬ በሀገሪቱ ግብረ ሰዶማውያንን በከፍተኛ ሁኔታ የሚቀጣ አዲስ ህግ በፊርማቸው አፅድቀዋል።
ይህ አዲስ ህግ ቀደም ሲል በግብረ ሰዶማዊነት ድርጊት ላይ ተጥሎ የነበረውን ከፍተኛ የእስር ቅጣት ወደ 10 ዓመት ከፍ አድርጎታል።
" ከተፈጥሮ ውጪ የሆኑ ድርጊቶች " ተብለው የተመደቡ የተመሳሳይ ፆታ ግንኙነቶች ላይ የሚጣለው ቅጣት ከነበረበት 1-5 ዓመት ወደ 5-10 ዓመት ከፍ እንዲል ተደርጓል።
አዲሱ ህግ ከእስር በተጨማሪ ከ2 ሚሊዮን እስከ 10 ሚሊዮን የሴኔጋል ፍራንክ ($3,500 - $17,600) የሚደርስ ከፍተኛ የገንዘብ መቀጮ ደንግጓል። ይህም ቀደም ሲል ከነበረው (1.5 ሚሊዮን ፍራንክ) እጅግ የላቀ ነው።
ግብረ ሰዶማዊነትን የሚያስተዋውቁ ወይም የገንዘብ ድጋፍ የሚያደርጉ ግለሰቦች ከ3 እስከ 7 ዓመት በሚደርስ እስራት እንዲቀጡ ህጉ ይፈቅዳል።
አፀያፊ የተባለውን ይህን ድርጊት የሚያበረታታ ማንኛውም ድርጊት እንደ ወንጀል እንዲታይ ተደርጓል።
ህጉ ያለምንም ማስረጃ ሌላውን ሰው በግብረ ሰዶማዊነት ወንጀል የሚከስ ማንኛውንም አካል በወንጀል እንደሚቀጣ አካቷል።
ይህ ጠንካራ ህግ ፕሬዝዳንት ባሲሩ ዲዮማዬ ፋዬ እና የሀገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ኡስማን ሶንኮ በምርጫ ወቅት ለህዝባቸው የገቡትን ቃል የፈጸሙበት ነው ተብሏል።
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብአዊ መብቶች ከፍተኛ ኮሚሽነር ቮልከር ቱርክ ውሳኔውን " እጅግ አሳሳቢ " ሲሉ የገለጹት ሲሆን ህጉ ሰብአዊ መብቶችን የሚጥስ መሆኑን ተናግረዋል።
በተቃራኒው በሴኔጋል የሚገኙ የሃይማኖት ተቋማት እና ማህበራት ግብረ ሰዶማዊነት "የምዕራባውያን ባህል መጫኛ መሳሪያ ነው" በሚል ጠንካራ ቅጣት እንዲጣል ሲወተውቱ ቆይተዋል ተብሏል።
ከባለፈው የካቲት ወር ጀምሮ በሴኔጋል በርካታ ሰዎች በግብረ ሰዶማዊነት ተጠርጥረው በቁጥጥር ስር ውለዋል።
አዲሱ ህግ ተጠርጣሪዎቹ ላይ የሚጣለውን ቅጣት የበለጠ በማክበድ በሀገሪቱ ያለውን ጥብቅ ቁጥጥር የሚያጠናክር ነው።
በተለይም ድርጊቱ የተፈጸመው ለአካለ መጠን ባልደረሱ ህፃናት ላይ ከሆነ ከፍተኛው ቅጣት እንደሚተገበር ህጉ ይገልጻል።
tikvahethiopia
2 months ago
''የአፍሪካ ዋንጫ ባለቤት ሞሮኮ በመሆኗ ደስ ብሎኛል'' አሽራፍ ሀኪሚ
#ethiopia | ሴኔጋል በሜዳ ላይ አሸንፋ የነበረ ቢሆንም፣ የካፍ (CAF) ይግባኝ ሰሚ ኮሚቴ በወሰነው ያልተጠበቀ ውሳኔ፣ ውጤቱን በመሻር ዋንጫውን በፎርፌ ለሞሮኮ መስጠቱ አይዘነጋም።
አሁን ደግሞ የሞሮኮ ብሔራዊ ቡድን አምበል አሽራፍ ሀኪሚ ዝምታውን ሰብሯል። ሀኪሚ ይህን የካፍ ውሳኔ እና የዋንጫ ድል በታላቅ ደስታ እንደሚቀበለው በይፋ ገልጿል።
“የአፍሪካ ዋንጫውን በዚህ መንገድ (በፎርፌ) ማሸነፍ ቢኖርብንም፣ በታላቅ ደስታ እንቀበለዋለን፤” ሲል አምበሉ ሀኪሚ ተናግሯል። አክሎም “በድሉ እጅግ በጣም ደስተኞች ነን፤ ይህንን ጊዜም ለረጅም ጊዜ ስጠብቀው ነበር” በማለት አስተያየቱን ሰጥቷል።
እርግጥ ነው፣ ነገሮች ገና እልባት አላገኙም! የካፍ የመጨረሻ ውሳኔ አሁን በዓለም አቀፉ የስፖርት ገላጋይ ፍርድ ቤት (TAS) ውሳኔ እንዲሰጥበት ተላልፏል። የሴኔጋል ይግባኝ ውጤቱን ሊቀለብሰው ይችላል ወይስ ሞሮኮ ዋንጫዋን በይፋ ታስቀራለች? በቀጣይ አዳዲስ መረጃዎች ሲወጡ የምናቀርብላችሁ ይሆናል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #afcon #hakimi #morocco #senegal #caf #tas #footballnews #abelbirhanu #ethiopiannews #sportupdates
#ethiopia | ሴኔጋል በሜዳ ላይ አሸንፋ የነበረ ቢሆንም፣ የካፍ (CAF) ይግባኝ ሰሚ ኮሚቴ በወሰነው ያልተጠበቀ ውሳኔ፣ ውጤቱን በመሻር ዋንጫውን በፎርፌ ለሞሮኮ መስጠቱ አይዘነጋም።
አሁን ደግሞ የሞሮኮ ብሔራዊ ቡድን አምበል አሽራፍ ሀኪሚ ዝምታውን ሰብሯል። ሀኪሚ ይህን የካፍ ውሳኔ እና የዋንጫ ድል በታላቅ ደስታ እንደሚቀበለው በይፋ ገልጿል።
“የአፍሪካ ዋንጫውን በዚህ መንገድ (በፎርፌ) ማሸነፍ ቢኖርብንም፣ በታላቅ ደስታ እንቀበለዋለን፤” ሲል አምበሉ ሀኪሚ ተናግሯል። አክሎም “በድሉ እጅግ በጣም ደስተኞች ነን፤ ይህንን ጊዜም ለረጅም ጊዜ ስጠብቀው ነበር” በማለት አስተያየቱን ሰጥቷል።
እርግጥ ነው፣ ነገሮች ገና እልባት አላገኙም! የካፍ የመጨረሻ ውሳኔ አሁን በዓለም አቀፉ የስፖርት ገላጋይ ፍርድ ቤት (TAS) ውሳኔ እንዲሰጥበት ተላልፏል። የሴኔጋል ይግባኝ ውጤቱን ሊቀለብሰው ይችላል ወይስ ሞሮኮ ዋንጫዋን በይፋ ታስቀራለች? በቀጣይ አዳዲስ መረጃዎች ሲወጡ የምናቀርብላችሁ ይሆናል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #afcon #hakimi #morocco #senegal #caf #tas #footballnews #abelbirhanu #ethiopiannews #sportupdates
2 months ago
የአፍሪካ ሕብረት የማኪ ሳልን የተባበሩት መንግሥታት ዋና ፀሐፊነት ዕጩነት ውድቅ ማድረጉ ተሰማ
#ethiopia | የአፍሪካ ሕብረት የቀድሞውን የሴኔጋል ፕሬዝዳንት ማኪ ሳልን ለተባበሩት መንግሥታት ዋና ፀሐፊነት ለማቅረብ የነበረውን የውሳኔ ሃሳብ ውድቅ ማድረጉ ተገለጠ።
ይህ ውሳኔ የተላለፈው ለጉዳዩ በተቀመጠው የ24 ሰዓታት የድምፅ አሰጣጥ የጊዜ ገደብ ውስጥ፣ 20 የሚጠጉ አባል አገራት የውሳኔ ሃሳቡን በመቃወም "ዝምታቸውን በመስበራቸው" መሆኑ ታውቋል። ይህም የዕጩነት ሂደቱ እንዳይጸድቅና ታግዶ እንዲቆይ አድርጎታል።
የአፍሪካ ሕብረት ጉባኤ ቢሮ ቀደም ሲል ባወጣው መረጃ፣ የማኪ ሳልን የአመራር ብቃትና በኃያላን አገራት መካከል መግባባትን የመፍጠር አቅማቸውን በመጥቀስ ዕጩነታቸው ተቀባይነት ያገኘ አስመስሎ ነበር። ሆኖም ግን፣ ትናንት በሕብረቱ የሴኔጋል ቋሚ መልዕክተኛ ቢሮ በሰጠው መግለጫ፣ የሴኔጋል መንግሥት የቀድሞው ፕሬዝዳንት ለዚህ ትልቅ ቦታ እንዲወዳደሩ በጭራሽ ድጋፍ ሰጥቶ እንደማያውቅ በማስታወቅ ጉዳዩን ይበልጥ አወዛጋቢ አድርጎታል።
ይህ ድንገተኛ ክስተት በአፍሪካ ሕብረት እና በሴኔጋል ወቅታዊ መንግሥት መካከል ያለውን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት እንዲሁም የአህጉሪቱን የጋራ ዕጩ የመምረጥ ሂደት ጥያቄ ውስጥ ከትቶታል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #africanunion #mackysall #unitednations #senegal #africanews #diplomacy #au #unsg
#ethiopia | የአፍሪካ ሕብረት የቀድሞውን የሴኔጋል ፕሬዝዳንት ማኪ ሳልን ለተባበሩት መንግሥታት ዋና ፀሐፊነት ለማቅረብ የነበረውን የውሳኔ ሃሳብ ውድቅ ማድረጉ ተገለጠ።
ይህ ውሳኔ የተላለፈው ለጉዳዩ በተቀመጠው የ24 ሰዓታት የድምፅ አሰጣጥ የጊዜ ገደብ ውስጥ፣ 20 የሚጠጉ አባል አገራት የውሳኔ ሃሳቡን በመቃወም "ዝምታቸውን በመስበራቸው" መሆኑ ታውቋል። ይህም የዕጩነት ሂደቱ እንዳይጸድቅና ታግዶ እንዲቆይ አድርጎታል።
የአፍሪካ ሕብረት ጉባኤ ቢሮ ቀደም ሲል ባወጣው መረጃ፣ የማኪ ሳልን የአመራር ብቃትና በኃያላን አገራት መካከል መግባባትን የመፍጠር አቅማቸውን በመጥቀስ ዕጩነታቸው ተቀባይነት ያገኘ አስመስሎ ነበር። ሆኖም ግን፣ ትናንት በሕብረቱ የሴኔጋል ቋሚ መልዕክተኛ ቢሮ በሰጠው መግለጫ፣ የሴኔጋል መንግሥት የቀድሞው ፕሬዝዳንት ለዚህ ትልቅ ቦታ እንዲወዳደሩ በጭራሽ ድጋፍ ሰጥቶ እንደማያውቅ በማስታወቅ ጉዳዩን ይበልጥ አወዛጋቢ አድርጎታል።
ይህ ድንገተኛ ክስተት በአፍሪካ ሕብረት እና በሴኔጋል ወቅታዊ መንግሥት መካከል ያለውን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት እንዲሁም የአህጉሪቱን የጋራ ዕጩ የመምረጥ ሂደት ጥያቄ ውስጥ ከትቶታል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #africanunion #mackysall #unitednations #senegal #africanews #diplomacy #au #unsg
2 months ago
የካሙዙ ካሳ ላላ መልዕክት
ሠላም ጤና ይስጥልኝ የተከበራችሁ ውድ ኢትዮጵያውያን
#ethiopia | በሀገራችን የፖለቲካ ታሪክ ጉምቱ የተባሉ የኪነጥበብ ባለሞያዎች እና በተለያዩ የሞያ ዘርፎች ላይ አንቱታን ያተረፉ ግለሰቦች ለህዝብ ጥቅም ለሀገር መፅናት ሲሉ በፖለቲካ ተሳትፈዉ ለህዝባቸዉ ይበጃል ያሉትን ታሪክ ሰርተዋል ፣ እየሰሩም ይገኛሉ። በአለም የፖለቲካ ጉዞም ቢሆን የኪነጥበብ ባለሞያዎች እና ስፖርተኞች ከረጅም ጊዜ ጀምሮ በማኅበራዊና ፖለቲካ ጉዳዮች ላይ ብርቱ ተሳትፎ ሲያደርጉ ቆይተዋል።
የነበራቸውን ተሳትፎ በወፍ በረር ለመቃኘት ያክል:-
————
ሴኔጋል – ኢሱኑ ንዱር (Youssou N'Dour)
በዓለም የሙዚቃ መድረክ ተወዳጁ የሴኔጋል ዘፋኝ ኢሱኑ ንዱር፣ ለረጅም ዓመታት በማኅበራዊ ጉዳዮች ላይ ድምጹን ካሰማ በኋላ፣ በ2012 የሴኔጋል የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ሆነው ተሾመ። በዚህ ሥልጣን የሀገሪቱን ቅርስ በማስጠበቅ ወጣቶችን በማብቃት ረገድ ትልቅ አሻራ አስቀርቷል።
————-
ላይቤሪያ – ጆርጅ ዊሃ (George Weah)
ከዓለም እግር ኳስ ታላላቅ ኮከቦች አንዱ የሆነው አፍሪካዊ የባሎን ዶር ተሸላሚ ጆርጅ ዌአ፣ ከሜዳ ጡረታ በኋላ ወደ ላይቤሪያ ፖለቲካ በመግባት ከፍተኛ ድምፅ በማግኘት በ2018 የሀገሪቱ ፕሬዚዳንት ሆኖ ተመረጠ። የእርሱ ጉዞ ከስፖርት ወደ ከፍተኛ የፖለቲካ አመራር ከሚታወቁት ደማቅ ምሳሌዎች አንዱ ነው።
—————
ናይጄሪያ – ፌላ ኩቲ (Fela Kuti)
የአፍሮቢት ሙዚቃ አባት ተብሎ የሚጠራው ናይጄሪያዊው ፌላ ኩቲ፣ በዘፈኖቹ ብቻ ሳይሆን በጠንካራ የፖለቲካ ንቅናቄውም ይታወቃል። መንግሥትን ጥሩ ሲሰራ ደግፎ በደልና ብልሹ አስተዳደርን በግልጽ ተቃዉሞ የካላኩታ ሪፐብሊክ በመባል በሚታወቀው ማኅበረሰቡ ውስጥ ተደጋጋሚ ቅጣትና እስራት ቢደርስበትም፣ የአፍሪካን የሕዝብ ተነሳሽነት በሙዚቃ አብይ ምሳሌ ሆኖ ቆይቷል።
——————
ዩናይትድ ስቴትስ – ሮናልድ ሬገን (Ronald Reagan)
ከሆሊዉድ ታዋቂ ተዋናዮች አንዱ የነበረው ሮናልድ ሬገን፣ ከስክሪን ወደ ፖለቲካ በመሻገር ከ1967 እስከ 1975 የካሊፎርኒያ ገዥ ሆኖ አገልግሏል፣ በኋላም በ1981 የአሜሪካ 40ኛ ፕሬዚዳንት ሆኖ ተመረጠ። በሁለት የሥልጣን ዘመኑ በቀዝቃዛው ጦርነት ማብቂያ ላይ ትልቅ ሚና በመጫወት፣ የአሜሪካን ኢኮኖሚ በሪጋኖሚክስ ፖሊሲ በማሻሻል ከተዋንያን ወደ ዓለም አለቃነት የተሸጋገሩ ብርቱ ምሳሌ ነዉ።
———————-
ቦብ ማርሊ (Bob Marley)
የሬጌ ሙዚቃ ምልክት ቦብ ማርሊ በዘፈኖቹ የሰላም፣ የአንድነትና የፖለቲካ ነፃነት መልእክት አሰማ። በጃማይካ ከፍተኛ የፖለቲካ ግጭት በነበረበት ወቅት ሁለት ተቀናቃኝ አንጃዎችን በአንድ መድረክ ላይ በማሰባሰብ “One Love” ኮንሰርት በማዘጋጀት ታሪካዊ ስራን ሰርቷል። ምንም እንኳ መደበኛ የፖለቲካ ሹመት ባይይዝም፣ በዓለም ዙሪያ እንደ ታላቅ የሰላም አራማጅና ተጽዕኖ ፈጣሪ ይታወሳል።
——————-//
ካሊፎርኒያ – አርኖልድ ሽዋርዜኔገር (Arnold Schwarzenegger)
በሆሊዉድ ፊልሞች ተወዳጁ የቀድሞ የሰውነት ግንባታ ሻምፒዮንና ተዋናይ አርኖልድ ሽዋርዜኔገር፣ ወደ ፖለቲካ በመግባት ከ2003 እስከ 2011 የካሊፎርኒያ ግዛት 38ኛ ገዥ ሆኖ አገልግሏል። በሁለት ወገን በተካሄደ ልዩ ምርጫ ተመርጦ፣ በአካባቢ ጥበቃና በጀት ማሻሻያ ላይ ትኩረት በማድረግ ከፊልም ስኬት ወደ እውነተኛ አመራር የተሻገረ ምሳሌ ነዉ።
———————-
ዩክሬን – ቮሎዲሚር ዘለንስኪ (Volodymyr Zelenskyy)
ዩክሬናዊው ኮሜዲያንና ተዋናይ ቮሎዲሚር ዘለንስኪ፣ በሰራዉ ተከታታይ ድራማ ውስጥ ፕሬዚዳንትን በመጫወት ታዋቂነትን ካገኘ በኋላ፣ በ2019 በእውነት የዩክሬን ፕሬዚዳንት ሆኖ ተመረጠ። ከሥልጣን ላይ በነበረበት ወቅት ሀገሩ ከባድ ጦርነት የገጠማት ሲሆን፣ ዘለንስኪ በአለም አቀፍ መድረክ የዩክሬንን ድምጽ በማሰማት የኮሜዲ ተዋናይነትን ወደ ጀግንነት የለወጠ አመራር አሳይቷል።
———————-
ቼክ ሪፐብሊክ – ቫችላቭ ሃቬል (Václav Havel)
የቼክ ጸሐፊ፣ ተውኔት ደራሲና የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ቫችላቭ ሃቬል፣ በኮሚኒስት አገዛዝ ዘመን በፅሑፎቹና በተግባሮቹ የሰላማዊ አብዮት (ቬልቬት አብዮት) መሪ ሆነ። ከአገዛዙ ውድቀት በኋላ በ1989 የቼኮዝሎቫኪያ ፕሬዚዳንት ሆኖተመረጠ፣ በኋላም የቼክ ሪፐብሊክ ፕሬዚዳንት ሆኖ እስከ 2003 አገልግሏል። የጸሐፊነት ብልሃቱን ወደ ዴሞክራሲ ግንባታ በመምራት ከባህል ወደ ፖለቲካ ከፍተኛ ለውጥ ካደረጉ ታላላቅ ሰዎች አንዱ
ነዉ።
ኔፓል ፣ ባለንድራ ሻህ(Balendra Shah) ፣
በሰፊው እሚታወቀዉ መጠሪያዉ Balen ነዉ፣ የቀድሞ ራፐር፣ ሂፕ-ሆፕ አርቲስት እና ስትራክቸራል መሐንዲስ ሲሆን ፣ የኔፓል አዲስ ብሔራዊ መሪ ሆኖ ተነስቷል። ይህም የባለን ፓርቲ የ Rastriya Swatantra Party (RSP) በማርች 5፣ 2026 ምርጫዎች ላይ ታሪካዊ አሸናፊነትን ተጎናፅፏል።
ባለንም በኔፓል ፖለቲካ ከወጣት መሪዎች አንዱ ያደርገዋል ።
———- #እናም የኪነጥበብ ባለሞያዎች በማኅበራዊና ፖለቲካዊ ጉዳዮች ላይ መሳተፍ ለሀገርና ለሕዝብ የጎላ ጥቅም ከማበርከት ባለፈ፣ ለኪነጥበብ ዘርፉ ከፍተኛ መነቃቃትን እንደሚፈጥር በጽኑ አምናለሁ ::ይሄም እድል ለኢትዮጵያ ኪነጥበብ እድገትም ትልቅ ሚና እንዳለው በማመንና አርቱን ሌሎች አገራት በደረሱበት ለማድረስ እንዲሁም ሀገርን በፅኑ ከማገልገል አላማ በመነሳት በተጨባጭ ለሀገር እየሰራ ነዉ ፣ ህዝቤን እና ሀገሬን ወደ ብልፅግና ማማ ያደርሳል ያልኩትን የብልጽግና ፓርቲን ወክዬ ለመወዳደር እጩ መሆኔን ሳበስር ደስታ ይሰማኛል።
—-////—-///—-
በስተመጨረሻም : እነሆ በኢትዮጵያ ታሪክ ወርቃማ ጊዜ ላይ እንገኛለን
የኢትዮጵያ ስብራቶች እየተጠገኑ ነው። በኢትዮጵያ እምቅ ሀብቶች እየወጡ ነው።
የኢትዮጵያ ጂኦ ፓለቲካዊ ቁመና እየተቀየረ ነው፣
ሀገር በምክክር እና በሽግግር ፍትህ ቁርሾዋን እየሻረች፣ ነገዋን እየተለመች ነው፣
ኢትዮጵያ በብዙ ነገሮች እራስዋን የመቻል ዕቅዷን እያሳካች ነው፣
የኢትዮጵያ ህልም እውን ሆኖ፣ ሁለንተናዊ ብልፅግና በኢትዮጵያ እንዲረጋገጥ፣ ጉዞው በውጤት ተጀምሯል።
ይሄን ውጤታማ ጉዞ ይበልጥ ለማሳካት ብልፅግናን መምረጥ ወሳኙ ነገር ነው።
ፈጣሪ ኢትዮጵያን ይባርክ!!!
ካሙዙ ካሣ
ሠላም ጤና ይስጥልኝ የተከበራችሁ ውድ ኢትዮጵያውያን
#ethiopia | በሀገራችን የፖለቲካ ታሪክ ጉምቱ የተባሉ የኪነጥበብ ባለሞያዎች እና በተለያዩ የሞያ ዘርፎች ላይ አንቱታን ያተረፉ ግለሰቦች ለህዝብ ጥቅም ለሀገር መፅናት ሲሉ በፖለቲካ ተሳትፈዉ ለህዝባቸዉ ይበጃል ያሉትን ታሪክ ሰርተዋል ፣ እየሰሩም ይገኛሉ። በአለም የፖለቲካ ጉዞም ቢሆን የኪነጥበብ ባለሞያዎች እና ስፖርተኞች ከረጅም ጊዜ ጀምሮ በማኅበራዊና ፖለቲካ ጉዳዮች ላይ ብርቱ ተሳትፎ ሲያደርጉ ቆይተዋል።
የነበራቸውን ተሳትፎ በወፍ በረር ለመቃኘት ያክል:-
————
ሴኔጋል – ኢሱኑ ንዱር (Youssou N'Dour)
በዓለም የሙዚቃ መድረክ ተወዳጁ የሴኔጋል ዘፋኝ ኢሱኑ ንዱር፣ ለረጅም ዓመታት በማኅበራዊ ጉዳዮች ላይ ድምጹን ካሰማ በኋላ፣ በ2012 የሴኔጋል የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ሆነው ተሾመ። በዚህ ሥልጣን የሀገሪቱን ቅርስ በማስጠበቅ ወጣቶችን በማብቃት ረገድ ትልቅ አሻራ አስቀርቷል።
————-
ላይቤሪያ – ጆርጅ ዊሃ (George Weah)
ከዓለም እግር ኳስ ታላላቅ ኮከቦች አንዱ የሆነው አፍሪካዊ የባሎን ዶር ተሸላሚ ጆርጅ ዌአ፣ ከሜዳ ጡረታ በኋላ ወደ ላይቤሪያ ፖለቲካ በመግባት ከፍተኛ ድምፅ በማግኘት በ2018 የሀገሪቱ ፕሬዚዳንት ሆኖ ተመረጠ። የእርሱ ጉዞ ከስፖርት ወደ ከፍተኛ የፖለቲካ አመራር ከሚታወቁት ደማቅ ምሳሌዎች አንዱ ነው።
—————
ናይጄሪያ – ፌላ ኩቲ (Fela Kuti)
የአፍሮቢት ሙዚቃ አባት ተብሎ የሚጠራው ናይጄሪያዊው ፌላ ኩቲ፣ በዘፈኖቹ ብቻ ሳይሆን በጠንካራ የፖለቲካ ንቅናቄውም ይታወቃል። መንግሥትን ጥሩ ሲሰራ ደግፎ በደልና ብልሹ አስተዳደርን በግልጽ ተቃዉሞ የካላኩታ ሪፐብሊክ በመባል በሚታወቀው ማኅበረሰቡ ውስጥ ተደጋጋሚ ቅጣትና እስራት ቢደርስበትም፣ የአፍሪካን የሕዝብ ተነሳሽነት በሙዚቃ አብይ ምሳሌ ሆኖ ቆይቷል።
——————
ዩናይትድ ስቴትስ – ሮናልድ ሬገን (Ronald Reagan)
ከሆሊዉድ ታዋቂ ተዋናዮች አንዱ የነበረው ሮናልድ ሬገን፣ ከስክሪን ወደ ፖለቲካ በመሻገር ከ1967 እስከ 1975 የካሊፎርኒያ ገዥ ሆኖ አገልግሏል፣ በኋላም በ1981 የአሜሪካ 40ኛ ፕሬዚዳንት ሆኖ ተመረጠ። በሁለት የሥልጣን ዘመኑ በቀዝቃዛው ጦርነት ማብቂያ ላይ ትልቅ ሚና በመጫወት፣ የአሜሪካን ኢኮኖሚ በሪጋኖሚክስ ፖሊሲ በማሻሻል ከተዋንያን ወደ ዓለም አለቃነት የተሸጋገሩ ብርቱ ምሳሌ ነዉ።
———————-
ቦብ ማርሊ (Bob Marley)
የሬጌ ሙዚቃ ምልክት ቦብ ማርሊ በዘፈኖቹ የሰላም፣ የአንድነትና የፖለቲካ ነፃነት መልእክት አሰማ። በጃማይካ ከፍተኛ የፖለቲካ ግጭት በነበረበት ወቅት ሁለት ተቀናቃኝ አንጃዎችን በአንድ መድረክ ላይ በማሰባሰብ “One Love” ኮንሰርት በማዘጋጀት ታሪካዊ ስራን ሰርቷል። ምንም እንኳ መደበኛ የፖለቲካ ሹመት ባይይዝም፣ በዓለም ዙሪያ እንደ ታላቅ የሰላም አራማጅና ተጽዕኖ ፈጣሪ ይታወሳል።
——————-//
ካሊፎርኒያ – አርኖልድ ሽዋርዜኔገር (Arnold Schwarzenegger)
በሆሊዉድ ፊልሞች ተወዳጁ የቀድሞ የሰውነት ግንባታ ሻምፒዮንና ተዋናይ አርኖልድ ሽዋርዜኔገር፣ ወደ ፖለቲካ በመግባት ከ2003 እስከ 2011 የካሊፎርኒያ ግዛት 38ኛ ገዥ ሆኖ አገልግሏል። በሁለት ወገን በተካሄደ ልዩ ምርጫ ተመርጦ፣ በአካባቢ ጥበቃና በጀት ማሻሻያ ላይ ትኩረት በማድረግ ከፊልም ስኬት ወደ እውነተኛ አመራር የተሻገረ ምሳሌ ነዉ።
———————-
ዩክሬን – ቮሎዲሚር ዘለንስኪ (Volodymyr Zelenskyy)
ዩክሬናዊው ኮሜዲያንና ተዋናይ ቮሎዲሚር ዘለንስኪ፣ በሰራዉ ተከታታይ ድራማ ውስጥ ፕሬዚዳንትን በመጫወት ታዋቂነትን ካገኘ በኋላ፣ በ2019 በእውነት የዩክሬን ፕሬዚዳንት ሆኖ ተመረጠ። ከሥልጣን ላይ በነበረበት ወቅት ሀገሩ ከባድ ጦርነት የገጠማት ሲሆን፣ ዘለንስኪ በአለም አቀፍ መድረክ የዩክሬንን ድምጽ በማሰማት የኮሜዲ ተዋናይነትን ወደ ጀግንነት የለወጠ አመራር አሳይቷል።
———————-
ቼክ ሪፐብሊክ – ቫችላቭ ሃቬል (Václav Havel)
የቼክ ጸሐፊ፣ ተውኔት ደራሲና የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ቫችላቭ ሃቬል፣ በኮሚኒስት አገዛዝ ዘመን በፅሑፎቹና በተግባሮቹ የሰላማዊ አብዮት (ቬልቬት አብዮት) መሪ ሆነ። ከአገዛዙ ውድቀት በኋላ በ1989 የቼኮዝሎቫኪያ ፕሬዚዳንት ሆኖተመረጠ፣ በኋላም የቼክ ሪፐብሊክ ፕሬዚዳንት ሆኖ እስከ 2003 አገልግሏል። የጸሐፊነት ብልሃቱን ወደ ዴሞክራሲ ግንባታ በመምራት ከባህል ወደ ፖለቲካ ከፍተኛ ለውጥ ካደረጉ ታላላቅ ሰዎች አንዱ
ነዉ።
ኔፓል ፣ ባለንድራ ሻህ(Balendra Shah) ፣
በሰፊው እሚታወቀዉ መጠሪያዉ Balen ነዉ፣ የቀድሞ ራፐር፣ ሂፕ-ሆፕ አርቲስት እና ስትራክቸራል መሐንዲስ ሲሆን ፣ የኔፓል አዲስ ብሔራዊ መሪ ሆኖ ተነስቷል። ይህም የባለን ፓርቲ የ Rastriya Swatantra Party (RSP) በማርች 5፣ 2026 ምርጫዎች ላይ ታሪካዊ አሸናፊነትን ተጎናፅፏል።
ባለንም በኔፓል ፖለቲካ ከወጣት መሪዎች አንዱ ያደርገዋል ።
———- #እናም የኪነጥበብ ባለሞያዎች በማኅበራዊና ፖለቲካዊ ጉዳዮች ላይ መሳተፍ ለሀገርና ለሕዝብ የጎላ ጥቅም ከማበርከት ባለፈ፣ ለኪነጥበብ ዘርፉ ከፍተኛ መነቃቃትን እንደሚፈጥር በጽኑ አምናለሁ ::ይሄም እድል ለኢትዮጵያ ኪነጥበብ እድገትም ትልቅ ሚና እንዳለው በማመንና አርቱን ሌሎች አገራት በደረሱበት ለማድረስ እንዲሁም ሀገርን በፅኑ ከማገልገል አላማ በመነሳት በተጨባጭ ለሀገር እየሰራ ነዉ ፣ ህዝቤን እና ሀገሬን ወደ ብልፅግና ማማ ያደርሳል ያልኩትን የብልጽግና ፓርቲን ወክዬ ለመወዳደር እጩ መሆኔን ሳበስር ደስታ ይሰማኛል።
—-////—-///—-
በስተመጨረሻም : እነሆ በኢትዮጵያ ታሪክ ወርቃማ ጊዜ ላይ እንገኛለን
የኢትዮጵያ ስብራቶች እየተጠገኑ ነው። በኢትዮጵያ እምቅ ሀብቶች እየወጡ ነው።
የኢትዮጵያ ጂኦ ፓለቲካዊ ቁመና እየተቀየረ ነው፣
ሀገር በምክክር እና በሽግግር ፍትህ ቁርሾዋን እየሻረች፣ ነገዋን እየተለመች ነው፣
ኢትዮጵያ በብዙ ነገሮች እራስዋን የመቻል ዕቅዷን እያሳካች ነው፣
የኢትዮጵያ ህልም እውን ሆኖ፣ ሁለንተናዊ ብልፅግና በኢትዮጵያ እንዲረጋገጥ፣ ጉዞው በውጤት ተጀምሯል።
ይሄን ውጤታማ ጉዞ ይበልጥ ለማሳካት ብልፅግናን መምረጥ ወሳኙ ነገር ነው።
ፈጣሪ ኢትዮጵያን ይባርክ!!!
ካሙዙ ካሣ
Sponsored by
Surafel
2 months ago
የሴኔጋልን የአፍሪካ ዋንጫ ድል የነጠቀው የካፍ ውሳኔ በጊዜያዊነት ታገደ!
#ethiopia | የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌደሬሽን (ካፍ) ሴኔጋልን ከ2025 የአፍሪካ ዋንጫ ሻምፒዮናነት የሻረበት አወዛጋቢ ውሳኔ በዓለም አቀፉ የስፖርት የግልግል ፍርድ ቤት (CAS) እገዳ ተጣለበት።
ጉዳዩ ምንድን ነው?
በጥር 2026 በሞሮኮ ረባት በተካሄደው የፍፃሜ ጨዋታ ሴኔጋል አስተናጋጇን ሞሮኮን 1 ለ 0 በማሸነፍ ዋንጫውን ማንሳቷ ይታወሳል። ሆኖም የካፍ ይግባኝ ሰሚ ኮሚቴ "በጨዋታው ማጠናቀቂያ ላይ በተሰጠ የፍፁም ቅጣት ምት ምክንያት የሴኔጋል ተጫዋቾች ለ17 ደቂቃ ሜዳውን ጥለው ወጥተዋል" በሚል ቡድኑ ጨዋታውን እንዳቋረጠ በመቁጠር ለሞሮኮ የ 3 ለ 0 የፎርፌ ድል ሰጥቶ ነበር።
ካፍ ዋንጫው ከሴኔጋል ተነጥቆ ለሞሮኮ እንዲሰጥ ያስተላለፈው ይህ ውሳኔ፣ በስፖርቱ ዓለም ከፍተኛ ተቃውሞን ሲቀሰቅስ የቆየ ሲሆን "የአፍሪካን እግር ኳስ ገፅታ ያበላሸ ነው" በሚል በብዙዎች ተወግዟል።
የ CAS ውሳኔ
የሴኔጋል እግር ኳስ ፌዴሬሽን "በሜዳ ላይ የተገኘ ውጤት በቢሮ ውሳኔ ሊቀየር አይገባም" በሚል ለዓለም አቀፉ የስፖርት የግልግል ፍርድ ቤት (CAS) ይግባኝ ማለቱን ተከትሎ፣ ፍርድ ቤቱ የካፍን ውሳኔ በጊዜያዊነት እንዲታገድ አዟል።
ፍርድ ቤቱ በጉዳዩ ላይ መርምሮ የመጨረሻ ውሳኔ ለመስጠት ከ9 እስከ 12 ወራት ሊፈጅበት እንደሚችል የተገለፀ ሲሆን፣ እስከዚያው ድረስ ግን የሴኔጋል የሻምፒዮናነት ክብር ጸንቶ ይቆያል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #senegal #morocco #caf #cas #afcon2025 #africacupofnations #footballnews #sportarbitration #senegalvsmorocco
#ethiopia | የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌደሬሽን (ካፍ) ሴኔጋልን ከ2025 የአፍሪካ ዋንጫ ሻምፒዮናነት የሻረበት አወዛጋቢ ውሳኔ በዓለም አቀፉ የስፖርት የግልግል ፍርድ ቤት (CAS) እገዳ ተጣለበት።
ጉዳዩ ምንድን ነው?
በጥር 2026 በሞሮኮ ረባት በተካሄደው የፍፃሜ ጨዋታ ሴኔጋል አስተናጋጇን ሞሮኮን 1 ለ 0 በማሸነፍ ዋንጫውን ማንሳቷ ይታወሳል። ሆኖም የካፍ ይግባኝ ሰሚ ኮሚቴ "በጨዋታው ማጠናቀቂያ ላይ በተሰጠ የፍፁም ቅጣት ምት ምክንያት የሴኔጋል ተጫዋቾች ለ17 ደቂቃ ሜዳውን ጥለው ወጥተዋል" በሚል ቡድኑ ጨዋታውን እንዳቋረጠ በመቁጠር ለሞሮኮ የ 3 ለ 0 የፎርፌ ድል ሰጥቶ ነበር።
ካፍ ዋንጫው ከሴኔጋል ተነጥቆ ለሞሮኮ እንዲሰጥ ያስተላለፈው ይህ ውሳኔ፣ በስፖርቱ ዓለም ከፍተኛ ተቃውሞን ሲቀሰቅስ የቆየ ሲሆን "የአፍሪካን እግር ኳስ ገፅታ ያበላሸ ነው" በሚል በብዙዎች ተወግዟል።
የ CAS ውሳኔ
የሴኔጋል እግር ኳስ ፌዴሬሽን "በሜዳ ላይ የተገኘ ውጤት በቢሮ ውሳኔ ሊቀየር አይገባም" በሚል ለዓለም አቀፉ የስፖርት የግልግል ፍርድ ቤት (CAS) ይግባኝ ማለቱን ተከትሎ፣ ፍርድ ቤቱ የካፍን ውሳኔ በጊዜያዊነት እንዲታገድ አዟል።
ፍርድ ቤቱ በጉዳዩ ላይ መርምሮ የመጨረሻ ውሳኔ ለመስጠት ከ9 እስከ 12 ወራት ሊፈጅበት እንደሚችል የተገለፀ ሲሆን፣ እስከዚያው ድረስ ግን የሴኔጋል የሻምፒዮናነት ክብር ጸንቶ ይቆያል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #senegal #morocco #caf #cas #afcon2025 #africacupofnations #footballnews #sportarbitration #senegalvsmorocco
3 months ago
ሴኔጋል የአፍሪካ ዋንጫዋን ተነጠቀች!
የታራንጋ አምበሶቹ አሳክተውት የነበረው የአፍሪካ ዋንጫ ለአትላስ አምበሶቹ አሳልፎ እንዲሰጥ ካፍ (CAF) ወስኗል። ይህ ውሳኔ በብዙዎች ዘንድ "ዘመን የማይሽረው አስቂኝ ውሳኔ" እየተባለ ይገኛል።
በቅርቡ በሞሮኮ አስተናጋጅነት በተካሄደው የአፍሪካ ዋንጫ ፍጻሜ፣ ሴኔጋል ሞሮኮን አሸንፋ ዋንጫውን ማንሳቷ ይታወሳል። በፍጻሜው ዕለት በተፈጠረ ውዝግብ ምክንያት ጨዋታው ለ17 ደቂቃ ተቋርጦ የነበረ ሲሆን፣ ጨዋታው እንደገና ከተጀመረ በኋላ ብራሂም ዲያዝ የፍፁም ቅጣት ምቱን ሆን ብሎ መሳቱን ተከትሎ፣ ሴኔጋል በፓፓ ጌ ባስቆጠራት ብቸኛ ግብ 1 ለ 0 አሸንፋ ነበር።
የሞሮኮ እግር ኳስ ፌዴሬሽን በፍጻሜው ዕለት የተፈጠረውን ውዝግብ መነሻ በማድረግ ለካፍ ይግባኝ ሰሚ ቦርድ ቅሬታውን አቅርቦ ቆይቷል። ጉዳዩን ሲመረምር የቆየው የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን (ካፍ) ይግባኝ ሰሚ ቦርድ፣ በአፍሪካ ዋንጫ ደንብ አንቀጽ 84 መሠረት የሴኔጋል ብሔራዊ ቡድን ተሸናፊ ሆኖ እንዲመዘገብ ወስኗል።
በዚህም መሠረት የጨዋታው ውጤት የሞሮኮ ብሔራዊ ቡድን 3 ለ 0 አሸናፊ ሆኖ እንዲመዘገብና ዋንጫውም ለሞሮኮ እንዲሰጥ ተወስኗል። ከእግር ኳስ ቤተሰቡ ዘንድ "ለካ ለዚህ ነው 'ባንዳው' የተባለው፤ ብራሂም ዲያዝ የፍፁም ቅጣት ምቱን ባይስተው ይሻል ነበር" የሚሉ አስተያየቶች እየተሰሙ ይገኛሉ።
ሴኔጋል ጉዳዩን ለዓለም አቀፉ የስፖርት የግልግል ፍርድ ቤት (CAS) መውሰድ አለባት የሚል እምነት በሰፊው ይንጸባረቃል። "በሜዳ ላይ አሸንፈህ ዋንጫ ተሰጥቶህ፣ በጓሮ በር ዋንጫ መነጠቅ አግባብ አይደለም" የሚሉ ወገኖች፣ የአፍሪካ እግር ኳስ አሁንም መብሰል የሚቀረውና በቧልተኛ አመራሮች የተሞላ መሆኑን ማሳያ ነው በማለት ቅሬታቸውን እየገለጹ ይገኛሉ።
seledadotio
seledadotio
የታራንጋ አምበሶቹ አሳክተውት የነበረው የአፍሪካ ዋንጫ ለአትላስ አምበሶቹ አሳልፎ እንዲሰጥ ካፍ (CAF) ወስኗል። ይህ ውሳኔ በብዙዎች ዘንድ "ዘመን የማይሽረው አስቂኝ ውሳኔ" እየተባለ ይገኛል።
በቅርቡ በሞሮኮ አስተናጋጅነት በተካሄደው የአፍሪካ ዋንጫ ፍጻሜ፣ ሴኔጋል ሞሮኮን አሸንፋ ዋንጫውን ማንሳቷ ይታወሳል። በፍጻሜው ዕለት በተፈጠረ ውዝግብ ምክንያት ጨዋታው ለ17 ደቂቃ ተቋርጦ የነበረ ሲሆን፣ ጨዋታው እንደገና ከተጀመረ በኋላ ብራሂም ዲያዝ የፍፁም ቅጣት ምቱን ሆን ብሎ መሳቱን ተከትሎ፣ ሴኔጋል በፓፓ ጌ ባስቆጠራት ብቸኛ ግብ 1 ለ 0 አሸንፋ ነበር።
የሞሮኮ እግር ኳስ ፌዴሬሽን በፍጻሜው ዕለት የተፈጠረውን ውዝግብ መነሻ በማድረግ ለካፍ ይግባኝ ሰሚ ቦርድ ቅሬታውን አቅርቦ ቆይቷል። ጉዳዩን ሲመረምር የቆየው የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን (ካፍ) ይግባኝ ሰሚ ቦርድ፣ በአፍሪካ ዋንጫ ደንብ አንቀጽ 84 መሠረት የሴኔጋል ብሔራዊ ቡድን ተሸናፊ ሆኖ እንዲመዘገብ ወስኗል።
በዚህም መሠረት የጨዋታው ውጤት የሞሮኮ ብሔራዊ ቡድን 3 ለ 0 አሸናፊ ሆኖ እንዲመዘገብና ዋንጫውም ለሞሮኮ እንዲሰጥ ተወስኗል። ከእግር ኳስ ቤተሰቡ ዘንድ "ለካ ለዚህ ነው 'ባንዳው' የተባለው፤ ብራሂም ዲያዝ የፍፁም ቅጣት ምቱን ባይስተው ይሻል ነበር" የሚሉ አስተያየቶች እየተሰሙ ይገኛሉ።
ሴኔጋል ጉዳዩን ለዓለም አቀፉ የስፖርት የግልግል ፍርድ ቤት (CAS) መውሰድ አለባት የሚል እምነት በሰፊው ይንጸባረቃል። "በሜዳ ላይ አሸንፈህ ዋንጫ ተሰጥቶህ፣ በጓሮ በር ዋንጫ መነጠቅ አግባብ አይደለም" የሚሉ ወገኖች፣ የአፍሪካ እግር ኳስ አሁንም መብሰል የሚቀረውና በቧልተኛ አመራሮች የተሞላ መሆኑን ማሳያ ነው በማለት ቅሬታቸውን እየገለጹ ይገኛሉ።
seledadotio
seledadotio
3 months ago
የአፍሪካ ዋንጫን የተነጠቀችው ሴኔጋል ካፍን በዓለም አቀፉ የስፖርት ፍርድ ቤት ልትከስ ነው
የሴኔጋል እግር ኳስ ፌዴሬሽን በካፍ ይግባኝ ሰሚ ኮሚቴ የተላለፈውን ውሳኔ በመቃወም ጉዳዩን ለዓለም አቀፉ የስፖርት የግልግል ፍርድ ቤት ለመውሰድ መወሰኑን አስታወቀ።
ካፍ ሞሮኮን የቅርብ ጊዜው የአፍሪካ ዋንጫ አሸናፊ በማድረግ ሴኔጋልን በ3-0 እንድትሸነፍ መወሰኑን ተከትሎ፣ የፌዴሬሽኑ ዋና ጸሐፊ አብዱላዬ ሶው ውሳኔውን "የእምነት ክህደት" ሲሉ ኮንነውታል።
ሶው እንደገለጹት፣ የቪዲዮ ኮንፈረንስ ችሎቱ የሴኔጋል ጠበቆች መዝጊያ ንግግር ሳያደርጉ በድንገት የተቋረጠ ሲሆን፣ ሂደቱም በከባድ ግድፈቶች የተሞላ ነው ብለዋል።
"ካፍ ሙስና ውስጥ ገብቷል" ያሉት ዋና ጸሐፊው፣ የሴኔጋልን ክብር ለማስጠበቅ እስከ መጨረሻው እንደሚታገሉና ዋንጫው ከሴኔጋል እንደማይወጣ አረጋግጠዋል።
አሁን ላይ የሁለቱ ወገኖች ክርክር በሊዛን በሚገኘው ፍርድ ቤት ውሳኔ የሚያገኝ ይሆናል።
የሴኔጋል እግር ኳስ ፌዴሬሽን በካፍ ይግባኝ ሰሚ ኮሚቴ የተላለፈውን ውሳኔ በመቃወም ጉዳዩን ለዓለም አቀፉ የስፖርት የግልግል ፍርድ ቤት ለመውሰድ መወሰኑን አስታወቀ።
ካፍ ሞሮኮን የቅርብ ጊዜው የአፍሪካ ዋንጫ አሸናፊ በማድረግ ሴኔጋልን በ3-0 እንድትሸነፍ መወሰኑን ተከትሎ፣ የፌዴሬሽኑ ዋና ጸሐፊ አብዱላዬ ሶው ውሳኔውን "የእምነት ክህደት" ሲሉ ኮንነውታል።
ሶው እንደገለጹት፣ የቪዲዮ ኮንፈረንስ ችሎቱ የሴኔጋል ጠበቆች መዝጊያ ንግግር ሳያደርጉ በድንገት የተቋረጠ ሲሆን፣ ሂደቱም በከባድ ግድፈቶች የተሞላ ነው ብለዋል።
"ካፍ ሙስና ውስጥ ገብቷል" ያሉት ዋና ጸሐፊው፣ የሴኔጋልን ክብር ለማስጠበቅ እስከ መጨረሻው እንደሚታገሉና ዋንጫው ከሴኔጋል እንደማይወጣ አረጋግጠዋል።
አሁን ላይ የሁለቱ ወገኖች ክርክር በሊዛን በሚገኘው ፍርድ ቤት ውሳኔ የሚያገኝ ይሆናል።
3 months ago
ሴኔጋል ያነሳችው የአፍሪካ ዋንጫ በካፍ ውሳኔ ለሞሮኮ ተሰጠ
የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን (ካፍ) ይግባኝ ሰሚ ጉባኤ ባሳለፈው አስገራሚ ውሳኔ፣ ሰኔጋል በሜዳ ላይ አሸንፋ የተቀዳጀችውን የ2025 የአፍሪካ ዋንጫ ክብር ተነጥቃለች።
ካፍ የሰኔጋል ብሔራዊ ቡድን የውድድሩን ደንቦች (አንቀጽ 82 እና 84) ጥሷል በሚል ክስ፣ የፍጻሜው ውጤት ተለውጦ ለሞሮኮ 3 ለ 0 በሆነ የቴክኒክ ድል እንዲመዘገብ ወስኗል።
ይህ በታሪክ ታይቶ የማይታወቅ ውሳኔ ሞሮኮን የዘንድሮው የአፍሪካ ዋንጫ አሸናፊ ሲያደርጋት፣ በስፖርቱ ዓለም ደግሞ ትልቅ መነጋገሪያ ሆኗል።
ጥር ላይ በነበረው የፍፃሜ ውድድር ሴነጋል ሞሮኮን አንድ ለ 0 አሸንፋ የነበረ ሲሆን መደበኛ ጨዋታ ሊጠናቀቅ ሲል ለሞሮኮ ፔናሊቲ ሲሰጥ የሴኔሌጋል ተጨዋቾች ፔናሊቲውን በመቃወም አንጫወትም ብለው ከሜዳ ወጥተው በአምበላቸው ሰይዱ ማኔ ሸምጋይነት ወደ ሜዳ መመለሳቸው ይታወሳል።
የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን (ካፍ) ይግባኝ ሰሚ ጉባኤ ባሳለፈው አስገራሚ ውሳኔ፣ ሰኔጋል በሜዳ ላይ አሸንፋ የተቀዳጀችውን የ2025 የአፍሪካ ዋንጫ ክብር ተነጥቃለች።
ካፍ የሰኔጋል ብሔራዊ ቡድን የውድድሩን ደንቦች (አንቀጽ 82 እና 84) ጥሷል በሚል ክስ፣ የፍጻሜው ውጤት ተለውጦ ለሞሮኮ 3 ለ 0 በሆነ የቴክኒክ ድል እንዲመዘገብ ወስኗል።
ይህ በታሪክ ታይቶ የማይታወቅ ውሳኔ ሞሮኮን የዘንድሮው የአፍሪካ ዋንጫ አሸናፊ ሲያደርጋት፣ በስፖርቱ ዓለም ደግሞ ትልቅ መነጋገሪያ ሆኗል።
ጥር ላይ በነበረው የፍፃሜ ውድድር ሴነጋል ሞሮኮን አንድ ለ 0 አሸንፋ የነበረ ሲሆን መደበኛ ጨዋታ ሊጠናቀቅ ሲል ለሞሮኮ ፔናሊቲ ሲሰጥ የሴኔሌጋል ተጨዋቾች ፔናሊቲውን በመቃወም አንጫወትም ብለው ከሜዳ ወጥተው በአምበላቸው ሰይዱ ማኔ ሸምጋይነት ወደ ሜዳ መመለሳቸው ይታወሳል።
Sponsored by
Surafel
3 months ago
ሴኔጋል ዋንጫዋን ተቀማች
ሞሮኮ የ2025 የአፍሪካ ዋንጫ (AFCON) አሸናፊ መሆኗን ካፍ አስታወቀ
በሞሮኮ አስተናጋጅነት በተካሄደው የ2025 የአፍሪካ ዋንጫ የፍፃሜ ጨዋታ ላይ በተፈጠረ ውዝግብ ዙሪያ የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን (CAF) የይግባኝ ሰሚ ኮሚቴ አስገራሚ ውሳኔ አሳልፏል። ሴኔጋል በቅጣት ጨዋታውን እንደተሸነፈች ተወስኖባታል።
በዚህም መሰረት አዘጋጇ ሀገር ሞሮኮ በአስተዳደራዊ ውሳኔ የውድድሩ አሸናፊ እና የዋንጫው ባለቤት ሆናለች።
የሞሮኮ እግር ኳስ ፌዴሬሽን (FRMF) ያቀረበውን ይግባኝ ለመመርመር የተሰበሰበው የይግባኝ ሰሚ ኮሚቴ የዲሲፕሊን ኮሚቴው ቀደም ብሎ ያስተላለፈውን ውሳኔ ሽሮታል።
ባለስልጣናቱ የአፍሪካ ዋንጫ ደንብ አንቀጽ 82 እና 84ን በመጥቀስንየሴኔጋል ብሔራዊ ቡድን ያሳየው ባህሪ ጠንካራ ቅጣት የሚያስቀጣ ነው በማለት ወስነዋል።
በዚህም ምክንያት ሴኔጋል በፍፃሜው ጨዋታ በሽንፈት (Forfeit) እንዲሰናበት ተደርጓል። በመሆኑም ይፋዊው ውጤት ሞሮኮን 3 ለ 0 አሸናፊ በሚያደርግ መልኩ ተመዝግቧል።
ሞሮኮ የ2025 የአፍሪካ ዋንጫ (AFCON) አሸናፊ መሆኗን ካፍ አስታወቀ
በሞሮኮ አስተናጋጅነት በተካሄደው የ2025 የአፍሪካ ዋንጫ የፍፃሜ ጨዋታ ላይ በተፈጠረ ውዝግብ ዙሪያ የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን (CAF) የይግባኝ ሰሚ ኮሚቴ አስገራሚ ውሳኔ አሳልፏል። ሴኔጋል በቅጣት ጨዋታውን እንደተሸነፈች ተወስኖባታል።
በዚህም መሰረት አዘጋጇ ሀገር ሞሮኮ በአስተዳደራዊ ውሳኔ የውድድሩ አሸናፊ እና የዋንጫው ባለቤት ሆናለች።
የሞሮኮ እግር ኳስ ፌዴሬሽን (FRMF) ያቀረበውን ይግባኝ ለመመርመር የተሰበሰበው የይግባኝ ሰሚ ኮሚቴ የዲሲፕሊን ኮሚቴው ቀደም ብሎ ያስተላለፈውን ውሳኔ ሽሮታል።
ባለስልጣናቱ የአፍሪካ ዋንጫ ደንብ አንቀጽ 82 እና 84ን በመጥቀስንየሴኔጋል ብሔራዊ ቡድን ያሳየው ባህሪ ጠንካራ ቅጣት የሚያስቀጣ ነው በማለት ወስነዋል።
በዚህም ምክንያት ሴኔጋል በፍፃሜው ጨዋታ በሽንፈት (Forfeit) እንዲሰናበት ተደርጓል። በመሆኑም ይፋዊው ውጤት ሞሮኮን 3 ለ 0 አሸናፊ በሚያደርግ መልኩ ተመዝግቧል።
3 months ago
ሰበር ዜና፡ የ2025 የአፍሪካ ዋንጫ አሸናፊ ተቀየረ ሞሮኮ ባለክብር ሆናለች!
#fastmereja I የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን (CAF) በ2025 የአፍሪካ ዋንጫ የፍጻሜ ጨዋታ ውጤት ላይ አስደንጋጭ ተብሎ የተገመተ አዲስ ውሳኔ አሳልፏል። የሴኔጋል ብሔራዊ ቡድን ጨዋታው ሳይጠናቀቅ ሜዳውን ጥሎ በመውጣቱ ምክንያት፣ ካፍ ጨዋታውን በሽንፈት (Forfeit) እንዲመዘገብ ወስኗል።
ካፍ ባስተላለፈው ውሳኔ መሠረት፣ ሞሮኮ የፍጻሜውን ጨዋታ 3 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸናፊ እንድትሆን ተደርጓል።
የሴኔጋል ተጫዋቾች በጨዋታው መሃል ሜዳውን ጥለው መውጣታቸው "የውድድር ደንብ መጣስ" ተብሎ በመፈረጁ፣ ቡድኑ ዋንጫውን እንዲያጣ ምክንያት ሆኗል።
በዚህም መሠረት የ2025 የአፍሪካ ዋንጫ ባለክብር ሞሮኮ መሆኗ በይፋ ተረጋግጧል።
#ስፖርት
#fastmereja I የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን (CAF) በ2025 የአፍሪካ ዋንጫ የፍጻሜ ጨዋታ ውጤት ላይ አስደንጋጭ ተብሎ የተገመተ አዲስ ውሳኔ አሳልፏል። የሴኔጋል ብሔራዊ ቡድን ጨዋታው ሳይጠናቀቅ ሜዳውን ጥሎ በመውጣቱ ምክንያት፣ ካፍ ጨዋታውን በሽንፈት (Forfeit) እንዲመዘገብ ወስኗል።
ካፍ ባስተላለፈው ውሳኔ መሠረት፣ ሞሮኮ የፍጻሜውን ጨዋታ 3 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸናፊ እንድትሆን ተደርጓል።
የሴኔጋል ተጫዋቾች በጨዋታው መሃል ሜዳውን ጥለው መውጣታቸው "የውድድር ደንብ መጣስ" ተብሎ በመፈረጁ፣ ቡድኑ ዋንጫውን እንዲያጣ ምክንያት ሆኗል።
በዚህም መሠረት የ2025 የአፍሪካ ዋንጫ ባለክብር ሞሮኮ መሆኗ በይፋ ተረጋግጧል።
#ስፖርት
3 months ago
ሴኔጋል ግብረ-ሰዶማዊነትን በከፍተኛ እስራት የሚያስቀጣ አዲስ ሕግ አጸደቀች
#fastmereja I የሴኔጋል ፓርላማ በሀገሪቱ ውስጥ ያሉ የግብረ-ሰዶማውያን ግንኙነቶችን የሚቀጣውን ከፍተኛ የእስራት ዘመን ከአምስት ዓመት ወደ 10 ዓመት ከፍ የሚያደርግ አዲስ ሕግ በሙሉ ድምፅ አጽድቋል።
በግብረ-ሰዶማዊነት ድርጊት የተገኘ ማንኛውም ሰው ከዚህ ቀደም ይጣልበት የነበረው የ5 ዓመት እስራት አሁን እስከ 10 ዓመት ሊደርስ ይችላል።
ጥፋተኞች ከ3,500 እስከ 17,600 የአሜሪካ ዶላር የሚደርስ የገንዘብ ቅጣት ይጠብቃቸዋል። ሕጉ ድርጊቱን መፈጸምን ብቻ ሳይሆን፣ የግብረ-ሰዶማውያን ግንኙነቶችን ማስተዋወቅ ወይም በገንዘብ መርዳትንም የወንጀል ድርጊት አድርጎታል። ለዚህም ከ3 እስከ 7 ዓመት የሚደርስ እስራት ይደነግጋል።
ድርጊቱ ለአቅመ-አዳም ያልደረሱ ህፃናትን የሚያካትት ከሆነ ከፍተኛው የቅጣት እርምጃ ተፈጻሚ ይሆናል።
አዲሱ ሕግ ያለበቂ ማስረጃ ሰዎችን በግብረ-ሰዶማዊነት በሀሰት የሚወነጅሉ ግለሰቦችንም በወንጀል የሚያስቀጣ አንቀጽ አካቷል።
ይህ ረቂቅ ሕግ በፓርላማው 135 ለ 0 በሆነ ድምፅ የፀደቀ ሲሆን፣ ሦስት ተወካዮች ደግሞ ድምፅ ከመስጠት ተቆጥበዋል። ሕጉ በጠቅላይ ሚኒስትር ኡስማን ሶንኮ አቅራቢነት ለፓርላማው የቀረበ ሲሆን፣ አሁን ተግባራዊ ለመሆን የፕሬዝዳንት ባሲሩ ዲዮማይ ፋዬን ፊርማ በመጠባበቅ ላይ ይገኛል።
#fastmereja I የሴኔጋል ፓርላማ በሀገሪቱ ውስጥ ያሉ የግብረ-ሰዶማውያን ግንኙነቶችን የሚቀጣውን ከፍተኛ የእስራት ዘመን ከአምስት ዓመት ወደ 10 ዓመት ከፍ የሚያደርግ አዲስ ሕግ በሙሉ ድምፅ አጽድቋል።
በግብረ-ሰዶማዊነት ድርጊት የተገኘ ማንኛውም ሰው ከዚህ ቀደም ይጣልበት የነበረው የ5 ዓመት እስራት አሁን እስከ 10 ዓመት ሊደርስ ይችላል።
ጥፋተኞች ከ3,500 እስከ 17,600 የአሜሪካ ዶላር የሚደርስ የገንዘብ ቅጣት ይጠብቃቸዋል። ሕጉ ድርጊቱን መፈጸምን ብቻ ሳይሆን፣ የግብረ-ሰዶማውያን ግንኙነቶችን ማስተዋወቅ ወይም በገንዘብ መርዳትንም የወንጀል ድርጊት አድርጎታል። ለዚህም ከ3 እስከ 7 ዓመት የሚደርስ እስራት ይደነግጋል።
ድርጊቱ ለአቅመ-አዳም ያልደረሱ ህፃናትን የሚያካትት ከሆነ ከፍተኛው የቅጣት እርምጃ ተፈጻሚ ይሆናል።
አዲሱ ሕግ ያለበቂ ማስረጃ ሰዎችን በግብረ-ሰዶማዊነት በሀሰት የሚወነጅሉ ግለሰቦችንም በወንጀል የሚያስቀጣ አንቀጽ አካቷል።
ይህ ረቂቅ ሕግ በፓርላማው 135 ለ 0 በሆነ ድምፅ የፀደቀ ሲሆን፣ ሦስት ተወካዮች ደግሞ ድምፅ ከመስጠት ተቆጥበዋል። ሕጉ በጠቅላይ ሚኒስትር ኡስማን ሶንኮ አቅራቢነት ለፓርላማው የቀረበ ሲሆን፣ አሁን ተግባራዊ ለመሆን የፕሬዝዳንት ባሲሩ ዲዮማይ ፋዬን ፊርማ በመጠባበቅ ላይ ይገኛል።
3 months ago
የሴኔጋል ጠቅላይ ሚኒስትር በተመሳሳይ ጾታ ግንኙነት ላይ የሚጣለውን ቅጣት ለመጨመር ቃል ገቡ
የሴኔጋል ጠቅላይ ሚኒስትር ኡስማን ሶንኮ፤ በተመሳሳይ ጾታ ግንኙነት ላይ የሚጣለውን ከፍተኛ ቅጣት እስከ አስር ዓመት እስራት የሚያደርስ ረቂቅ ሕግ ይፋ አድርገዋል።
ይህ ረቂቅ ሕግ ‹‹ለተመሳሳይ ጾታ ግንኙነት ቅስቀሳ በሚያደርግ›› ማንኛውም ሰው ላይ ከሶስት እስከ ሰባት ዓመት የሚደርስ እስራት ይጥላል።
ኡስማን ሶንኮ ለፓርላማው ሲናገሩ ማንኛውም ‹‹ከተፈጥሮ ውጪ የሆነ ድርጊት›› የሚፈጽም ሰው ከአምስት እስከ 10 ዓመት በሚደርስ ጽኑ እስራት ይቀጣል ብለዋል።
በተመሳሳይ ጾታ ግንኙነት የተጠረጠሩ ሰዎች በቁጥጥር ስር መዋልን ተከትሎ፤ ሚኒስትሮች ረቂቅ ሕጉን ባለፈው ሳምንት ለፓርላማው መርተውታል።
በቁጥጥር ስር ከዋሉት መካከል ሁለት የአገር ውስጥ ታዋቂ ሰዎችና አንድ የታወቀ ጋዜጠኛ ይገኙበታል።
ይህ ውሳኔ የመጣው ባለፉት ጥቂት ዓመታት የሃይማኖት ድርጅቶች ጠንከር ያለ ቅጣት እንዲጣል በመጠየቅ ተቃውሞ ሲያደርጉ ከቆዩ በኋላ ነው።
በፓርላማው ድምጽ የሚሰጥበት ቀን እስካሁን አልተቆረጠም ያለዉ አፍሪካ ኒዉስ ነዉ።
Ethio Fm
የሴኔጋል ጠቅላይ ሚኒስትር ኡስማን ሶንኮ፤ በተመሳሳይ ጾታ ግንኙነት ላይ የሚጣለውን ከፍተኛ ቅጣት እስከ አስር ዓመት እስራት የሚያደርስ ረቂቅ ሕግ ይፋ አድርገዋል።
ይህ ረቂቅ ሕግ ‹‹ለተመሳሳይ ጾታ ግንኙነት ቅስቀሳ በሚያደርግ›› ማንኛውም ሰው ላይ ከሶስት እስከ ሰባት ዓመት የሚደርስ እስራት ይጥላል።
ኡስማን ሶንኮ ለፓርላማው ሲናገሩ ማንኛውም ‹‹ከተፈጥሮ ውጪ የሆነ ድርጊት›› የሚፈጽም ሰው ከአምስት እስከ 10 ዓመት በሚደርስ ጽኑ እስራት ይቀጣል ብለዋል።
በተመሳሳይ ጾታ ግንኙነት የተጠረጠሩ ሰዎች በቁጥጥር ስር መዋልን ተከትሎ፤ ሚኒስትሮች ረቂቅ ሕጉን ባለፈው ሳምንት ለፓርላማው መርተውታል።
በቁጥጥር ስር ከዋሉት መካከል ሁለት የአገር ውስጥ ታዋቂ ሰዎችና አንድ የታወቀ ጋዜጠኛ ይገኙበታል።
ይህ ውሳኔ የመጣው ባለፉት ጥቂት ዓመታት የሃይማኖት ድርጅቶች ጠንከር ያለ ቅጣት እንዲጣል በመጠየቅ ተቃውሞ ሲያደርጉ ከቆዩ በኋላ ነው።
በፓርላማው ድምጽ የሚሰጥበት ቀን እስካሁን አልተቆረጠም ያለዉ አፍሪካ ኒዉስ ነዉ።
Ethio Fm
3 months ago
🇸🇳 ሴኔጋል በተመሳሳይ ጾታ ግንኙነት ላይ የሚጣለው እስራት በእጥፍ ልትጨምር ነው
#ethiopia | የሴኔጋል የሚኒስትሮች ምክር ቤት "ተፈጥሯዊ ያልሆነ ድርጊት" በሚል በፈረጀው የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነት ላይ የሚጣለውን ቅጣት በከፍተኛ ሁኔታ የሚጨምር አዲስ ረቂቅ አዋጅ አጽድቋል። ይህ ውሳኔ በፓርላማው ሲጸድቅ ሙሉ በሙሉ ወደ ተግባር የሚገባ ይሆናል።
የሀገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ኦስማን ሶንኮ በምርጫ ቅስቀሳ ወቅት የገቡትን ቃል መሠረት በማድረግ የቀረበው ይህ ማሻሻያ፣ የሚከተሉትን ዋና ዋና ነጥቦች አካቷል፦
⚖️ ዋና ዋና የቅጣት ማሻሻያዎች
የእስር ጊዜ - እስከ 5 ዓመት ወደ 10 ዓመት
የገንዘብ ቅጣት -ከ1.5 ሚሊዮን ፍራንክ ወደ 10 ሚሊዮን ፍራንክ
🚫 "LGBT"ን ማስተዋወቅ ያስቀጣል
የሴኔጋል የባህል ሚኒስትር እንዳስታወቁት፣ ድርጊቱን መፈጸም ብቻ ሳይሆን "LGBT"ን በተለያዩ መንገዶች የሚያራምዱ አካላት ላይ እርምጃ ይወሰዳል። ይህም የሚከተሉትን ያጠቃልላል፦
* በፊልሞች እና በቴሌቪዥን ፕሮግራሞች አማካኝነት ማስተዋወቅ።
* በጽሁፎች ወይም በሌሎች የሚዲያ ውጤቶች ዘመቻ ማድረግ።
* ተግባሩን የሚያበረታቱ ተቋማት እና ቡድኖች ላይ ተጠያቂነትን ማስፈን።
🛡️ ከሀሰት ክስ መከላከያ
በሌላ በኩል፣ ህጉ ያለ በቂ ማስረጃ ሰዎችን "ተመሳሳይ ጾታ ግንኙነት ፈጻሚዎች ናቸው" ብሎ በሀሰት መወንጀልንም ወንጀል አድርጎታል።
በዚህ ድርጊት የተገኘ ሰው ከ2 እስከ 3 ዓመት በሚደርስ እስራት እና ከ200 ሺህ እስከ 500 ሺህ ፍራንክ በሚደርስ የገንዘብ ቅጣት ይቀጣል።
ይህ እርምጃ ሴኔጋል የራሷን ባህላዊ እና ማህበራዊ እሴቶች ለመጠበቅ የወሰደችው አቋም መሆኑን መንግስት ገልጿል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #ሴኔጋል #senegal #lgbtq #የህግማሻሻያ #አፍሪካ #ዜና
#ethiopia | የሴኔጋል የሚኒስትሮች ምክር ቤት "ተፈጥሯዊ ያልሆነ ድርጊት" በሚል በፈረጀው የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነት ላይ የሚጣለውን ቅጣት በከፍተኛ ሁኔታ የሚጨምር አዲስ ረቂቅ አዋጅ አጽድቋል። ይህ ውሳኔ በፓርላማው ሲጸድቅ ሙሉ በሙሉ ወደ ተግባር የሚገባ ይሆናል።
የሀገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ኦስማን ሶንኮ በምርጫ ቅስቀሳ ወቅት የገቡትን ቃል መሠረት በማድረግ የቀረበው ይህ ማሻሻያ፣ የሚከተሉትን ዋና ዋና ነጥቦች አካቷል፦
⚖️ ዋና ዋና የቅጣት ማሻሻያዎች
የእስር ጊዜ - እስከ 5 ዓመት ወደ 10 ዓመት
የገንዘብ ቅጣት -ከ1.5 ሚሊዮን ፍራንክ ወደ 10 ሚሊዮን ፍራንክ
🚫 "LGBT"ን ማስተዋወቅ ያስቀጣል
የሴኔጋል የባህል ሚኒስትር እንዳስታወቁት፣ ድርጊቱን መፈጸም ብቻ ሳይሆን "LGBT"ን በተለያዩ መንገዶች የሚያራምዱ አካላት ላይ እርምጃ ይወሰዳል። ይህም የሚከተሉትን ያጠቃልላል፦
* በፊልሞች እና በቴሌቪዥን ፕሮግራሞች አማካኝነት ማስተዋወቅ።
* በጽሁፎች ወይም በሌሎች የሚዲያ ውጤቶች ዘመቻ ማድረግ።
* ተግባሩን የሚያበረታቱ ተቋማት እና ቡድኖች ላይ ተጠያቂነትን ማስፈን።
🛡️ ከሀሰት ክስ መከላከያ
በሌላ በኩል፣ ህጉ ያለ በቂ ማስረጃ ሰዎችን "ተመሳሳይ ጾታ ግንኙነት ፈጻሚዎች ናቸው" ብሎ በሀሰት መወንጀልንም ወንጀል አድርጎታል።
በዚህ ድርጊት የተገኘ ሰው ከ2 እስከ 3 ዓመት በሚደርስ እስራት እና ከ200 ሺህ እስከ 500 ሺህ ፍራንክ በሚደርስ የገንዘብ ቅጣት ይቀጣል።
ይህ እርምጃ ሴኔጋል የራሷን ባህላዊ እና ማህበራዊ እሴቶች ለመጠበቅ የወሰደችው አቋም መሆኑን መንግስት ገልጿል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #ሴኔጋል #senegal #lgbtq #የህግማሻሻያ #አፍሪካ #ዜና
Sponsored by
Surafel
4 months ago
♦️ካፍ በታሪኩ ከፍተኛ የተባለውን ቅጣት ሴኔጋልና ሞሮኮ ላይ አሳረፈ
✍️✍️በጋዜጠኛ ይስሀቅ በላይ
(ሀትሪክ ስፖርት ኦፊሺያል)
የአፍሪካን እግር ኳስ በበላይነት የሚመራው ካፍ ለ35ተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ፍፃሜ ደርሠው ያልተገባ ባህሪ አሳይተዋል የተባሉት አዘጋጅዋ ሞሮኮና ሴኔጋል ላይ በታሪኩ ከፍተኛ የተባለውን ቅጣት አስተላልፏል።
♦️የካፍ ውሳኔ በሴኔጋል ላይ 🇸🇳
1. በሴኔጋል ደጋፊዎች ላይ በታየ ያልተገባ ባህሪ $300 000(ዶላር)
2. በሴኔጋል ተጫዋቾችና የቡድን አባላት ላይ በታየ ያልተገባ ባህሪ $300 000(ዶላር)
3. በፍፃሜ ጨዋታ ቢጫ ካርድ ባዩ የሴኔጋል ተጫዋቾች ላይ $15000(ዶላር)
4. ፔፕ ታህያው የሴኔጋል ብ/ቡድን ዋና አሠልጣኝ የ$100 000 ዶላርና 5 የካፍ ኦፊሺያል ጨዋታዎች ዕገዳ
5. ሊይማን ኒዲያዬ እና ኢስማይላ ሳር የዕለቱ የመሀል ዳኛ ላይ ጥቃት በመፈፀማቸው፣
♦️የካፍ ውሳኔ በሞሮኮ ላይ🇲🇦
1. የጨዋታው ኳስ አቀባዮች(Ball boys) ያልተገባ ባህሪ በማሳየታቸው $200 000(ዶላር)
2. በሞሮኮ ተጫዋቾችና የቡድን አባላት ላይ በታየ ያልተገባ ባህሪ $100 000(ዶላር)
3. ደጋፊዎች ላሳዩት ያልተገባ ባህሪ $15 000(ዶላር)
4. የሞሮኮው አሽራፍ ሀኪሚ ባሳየው ያልተገባ ባህሪ ሁለት የካፍ ኦፊሺያል ጨዋታዎች ቅጣት
5.ኢስመማኤል ሳይባሪ ባሳየው ያልተገባ ባህሪ ሶስት የካፍ ኦፊሺያል ጨዋታዎች ቅጣት ከማስተላለፉም በላይ የሞሮኮን ይግባኝ ውድቅ አድርጎ የሴኔጋል ሻምፒዮናነት አውጇል።
✍️✍️በጋዜጠኛ ይስሀቅ በላይ
(ሀትሪክ ስፖርት ኦፊሺያል)
የአፍሪካን እግር ኳስ በበላይነት የሚመራው ካፍ ለ35ተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ፍፃሜ ደርሠው ያልተገባ ባህሪ አሳይተዋል የተባሉት አዘጋጅዋ ሞሮኮና ሴኔጋል ላይ በታሪኩ ከፍተኛ የተባለውን ቅጣት አስተላልፏል።
♦️የካፍ ውሳኔ በሴኔጋል ላይ 🇸🇳
1. በሴኔጋል ደጋፊዎች ላይ በታየ ያልተገባ ባህሪ $300 000(ዶላር)
2. በሴኔጋል ተጫዋቾችና የቡድን አባላት ላይ በታየ ያልተገባ ባህሪ $300 000(ዶላር)
3. በፍፃሜ ጨዋታ ቢጫ ካርድ ባዩ የሴኔጋል ተጫዋቾች ላይ $15000(ዶላር)
4. ፔፕ ታህያው የሴኔጋል ብ/ቡድን ዋና አሠልጣኝ የ$100 000 ዶላርና 5 የካፍ ኦፊሺያል ጨዋታዎች ዕገዳ
5. ሊይማን ኒዲያዬ እና ኢስማይላ ሳር የዕለቱ የመሀል ዳኛ ላይ ጥቃት በመፈፀማቸው፣
♦️የካፍ ውሳኔ በሞሮኮ ላይ🇲🇦
1. የጨዋታው ኳስ አቀባዮች(Ball boys) ያልተገባ ባህሪ በማሳየታቸው $200 000(ዶላር)
2. በሞሮኮ ተጫዋቾችና የቡድን አባላት ላይ በታየ ያልተገባ ባህሪ $100 000(ዶላር)
3. ደጋፊዎች ላሳዩት ያልተገባ ባህሪ $15 000(ዶላር)
4. የሞሮኮው አሽራፍ ሀኪሚ ባሳየው ያልተገባ ባህሪ ሁለት የካፍ ኦፊሺያል ጨዋታዎች ቅጣት
5.ኢስመማኤል ሳይባሪ ባሳየው ያልተገባ ባህሪ ሶስት የካፍ ኦፊሺያል ጨዋታዎች ቅጣት ከማስተላለፉም በላይ የሞሮኮን ይግባኝ ውድቅ አድርጎ የሴኔጋል ሻምፒዮናነት አውጇል።
4 months ago
🚨 ካፍ በሞሮኮ እና ሴኔጋል ላይ የቅጣት ናዳ አወረደ!
#ethiopia | በሞሮኮ አስተናጋጅነት በተካሄደው የአፍሪካ ዋንጫ የፍፃሜ ጨዋታ ላይ የታዩት ያልተገቡ ስፖርታዊ ክስተቶች የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽንን (ካፍ) ክፉኛ አስቆጥተዋል። ተቋሙ በሁለቱም ብሔራዊ ቡድኖች፣ ተጫዋቾች እና አሰልጣኞች ላይ ጠንከር ያሉ የዲሲፕሊን እርምጃዎችን መውሰዱን በይፋ አስታውቋል።
በውሳኔው መሰረት የተላለፉት ቅጣቶች የሚከተሉት ናቸው፡
🇸🇳 በሴኔጋል ብሔራዊ ቡድን ላይ የተጣሉ ቅጣቶች፡
የአንበሶቹ ካምፕ ከፍተኛ የገንዘብ እና የእገዳ ቅጣት ሰለባ ሆኗል።
* አሰልጣኝ ፓፔ ቲያው፡ በ5 የካፍ ጨዋታዎች ላይ እንዳይሳተፉ ከመታገዳቸውም በላይ 100,000 ዶላር የገንዘብ ቅጣት ተጥሎባቸዋል።
* ተጫዋቾች፡ ኢልማን ንዳዬ እና እስማኤል ሳር ለ2 ጨዋታዎች እንዲታገዱ ተወስኗል።
* የሴኔጋል እግር ኳስ ፌዴሬሽን፡ በጠቅላላው 615,000 ዶላር እንዲከፍል ተበይኖበታል።
🇲🇦 በሞሮኮ ብሔራዊ ቡድን ላይ የተጣሉ ቅጣቶች፡
አስተናጋጇ ሞሮኮም ከካፍ ቁጣ አላመለጠችም፤ ቁልፍ ተጫዋቾቿ የእገዳ ሰለባ ሆነዋል።
* አሽራፍ ሀኪሚ፡ የቡድኑ ኮከብ ለ2 ጨዋታዎች ታግዷል።
* እስማኤል ሳይባሪ፡ ለ3 ጨዋታዎች ከሜዳ እንዲርቅ ተወስኖበታል።
* የሞሮኮ እግር ኳስ ፌዴሬሽን፡ 315,000 ዶላር የገንዘብ ቅጣት ተላልፎበታል።
እነዚህ ቅጣቶች በስፖርቱ ዓለም የሚታዩ ያልተገቡ ባህሪዎችን ለመግታት እና "Fair Play" እንዲከበር ለማድረግ የተወሰዱ እርምጃዎች መሆናቸው ተገልጿል። ስፖርት በሜዳ ላይ በሚታይ ብቃት እንጂ ከጨዋታ ውጭ በሚደረጉ ግጭቶች መደምደም እንደሌለበት ትልቅ ትምህርት የሰጠ ውሳኔ ይመስላል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #caf #afcon #morocco #senegal #footballnews #africacupofnations #ካፍ #የአፍሪካዋንጫ #ሞሮኮ #ሴኔጋል
#ethiopia | በሞሮኮ አስተናጋጅነት በተካሄደው የአፍሪካ ዋንጫ የፍፃሜ ጨዋታ ላይ የታዩት ያልተገቡ ስፖርታዊ ክስተቶች የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽንን (ካፍ) ክፉኛ አስቆጥተዋል። ተቋሙ በሁለቱም ብሔራዊ ቡድኖች፣ ተጫዋቾች እና አሰልጣኞች ላይ ጠንከር ያሉ የዲሲፕሊን እርምጃዎችን መውሰዱን በይፋ አስታውቋል።
በውሳኔው መሰረት የተላለፉት ቅጣቶች የሚከተሉት ናቸው፡
🇸🇳 በሴኔጋል ብሔራዊ ቡድን ላይ የተጣሉ ቅጣቶች፡
የአንበሶቹ ካምፕ ከፍተኛ የገንዘብ እና የእገዳ ቅጣት ሰለባ ሆኗል።
* አሰልጣኝ ፓፔ ቲያው፡ በ5 የካፍ ጨዋታዎች ላይ እንዳይሳተፉ ከመታገዳቸውም በላይ 100,000 ዶላር የገንዘብ ቅጣት ተጥሎባቸዋል።
* ተጫዋቾች፡ ኢልማን ንዳዬ እና እስማኤል ሳር ለ2 ጨዋታዎች እንዲታገዱ ተወስኗል።
* የሴኔጋል እግር ኳስ ፌዴሬሽን፡ በጠቅላላው 615,000 ዶላር እንዲከፍል ተበይኖበታል።
🇲🇦 በሞሮኮ ብሔራዊ ቡድን ላይ የተጣሉ ቅጣቶች፡
አስተናጋጇ ሞሮኮም ከካፍ ቁጣ አላመለጠችም፤ ቁልፍ ተጫዋቾቿ የእገዳ ሰለባ ሆነዋል።
* አሽራፍ ሀኪሚ፡ የቡድኑ ኮከብ ለ2 ጨዋታዎች ታግዷል።
* እስማኤል ሳይባሪ፡ ለ3 ጨዋታዎች ከሜዳ እንዲርቅ ተወስኖበታል።
* የሞሮኮ እግር ኳስ ፌዴሬሽን፡ 315,000 ዶላር የገንዘብ ቅጣት ተላልፎበታል።
እነዚህ ቅጣቶች በስፖርቱ ዓለም የሚታዩ ያልተገቡ ባህሪዎችን ለመግታት እና "Fair Play" እንዲከበር ለማድረግ የተወሰዱ እርምጃዎች መሆናቸው ተገልጿል። ስፖርት በሜዳ ላይ በሚታይ ብቃት እንጂ ከጨዋታ ውጭ በሚደረጉ ግጭቶች መደምደም እንደሌለበት ትልቅ ትምህርት የሰጠ ውሳኔ ይመስላል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #caf #afcon #morocco #senegal #footballnews #africacupofnations #ካፍ #የአፍሪካዋንጫ #ሞሮኮ #ሴኔጋል
4 months ago
🇸🇳 የሴኔጋል "አንበሶች" በሽልማት ተንበሸበሹ! 🦁💰
#ethiopia | የአፍሪካ እግር ኳስ ንጉሥነታቸውን ያስመሰከሩት የሴኔጋል ብሔራዊ ቡድን አባላት፣ በሀገሪቱ ወጣት ፕሬዝዳንት ባሲሩ ዲዮማዬ ፋዬ አማካኝነት በታሪክ የማይረሳ እና እጅግ ድንቅ የሆነ የክብር አቀባበል እንዲሁም የሽልማት ናዳ ወርዶባቸዋል።
ፕሬዝዳንቱ ለቡድኑ አባላት ካበረከቱት ፈርጀ ብዙ ሽልማቶች መካከል ዋና ዋናዎቹ፦
💵 የገንዘብ ሽልማት፦
* ለቡድኑ አባላት በጥሬ ገንዘብ 535,000 ዶላር ተበርክቷል።
* እያንዳንዱ ተጫዋች ለቤት መስሪያ የሚሆን 135,000 ዶላር ተጨማሪ ስጦታ አግኝቷል።
* ለአሰልጣኞች እና ለቡድን አጋዥ አባላት ደግሞ 90,000 ዶላር ተሰጥቷል።
🏗️ የመሬት ስጦታ፦
* ለእያንዳንዱ ተጫዋች በዋና ከተማዋ ዳካር መሐል 1,500 ካሬ ሜትር ስፋት ያለው መሬት።
* ለአሰልጣኝ ቡድኑ አባላት 1,000 ካሬ ሜትር መሬት።
* በአጠቃላይ መንግስት 68,000 ካሬ ሜትር መሬት ለቡድኑ አባላት በስም አዙሯል።
🎖️ የክብር ማዕረግ፦
ከገንዘብ እና ከመሬት ስጦታው ባለፈ፣ ፕሬዝዳንቱ ለታሪካዊው ድል ባለቤቶች የሀገሪቱን ከፍተኛ የክብር "የኮማንደር ማዕረግ" (National Order of the Lion) ሰጥተዋል።
በድምሩ የሴኔጋል መንግስት ከ 6.2 ሚሊዮን ዶላር በላይ ለዚህ ድል ወጪ ማድረጉ ታውቋል። ይህ እርምጃ ሀገሪቱ ለስፖርቱ ያላትን ትልቅ ክብር እና ለወጣቶቿ የምትሰጠውን ማበረታቻ በግልጽ ያሳየ ሆኗል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#senegal #africanchampions #bassiroudiomayefaye #terangalions #footballnews #africacup #inspiration #ethiopia
#ethiopia | የአፍሪካ እግር ኳስ ንጉሥነታቸውን ያስመሰከሩት የሴኔጋል ብሔራዊ ቡድን አባላት፣ በሀገሪቱ ወጣት ፕሬዝዳንት ባሲሩ ዲዮማዬ ፋዬ አማካኝነት በታሪክ የማይረሳ እና እጅግ ድንቅ የሆነ የክብር አቀባበል እንዲሁም የሽልማት ናዳ ወርዶባቸዋል።
ፕሬዝዳንቱ ለቡድኑ አባላት ካበረከቱት ፈርጀ ብዙ ሽልማቶች መካከል ዋና ዋናዎቹ፦
💵 የገንዘብ ሽልማት፦
* ለቡድኑ አባላት በጥሬ ገንዘብ 535,000 ዶላር ተበርክቷል።
* እያንዳንዱ ተጫዋች ለቤት መስሪያ የሚሆን 135,000 ዶላር ተጨማሪ ስጦታ አግኝቷል።
* ለአሰልጣኞች እና ለቡድን አጋዥ አባላት ደግሞ 90,000 ዶላር ተሰጥቷል።
🏗️ የመሬት ስጦታ፦
* ለእያንዳንዱ ተጫዋች በዋና ከተማዋ ዳካር መሐል 1,500 ካሬ ሜትር ስፋት ያለው መሬት።
* ለአሰልጣኝ ቡድኑ አባላት 1,000 ካሬ ሜትር መሬት።
* በአጠቃላይ መንግስት 68,000 ካሬ ሜትር መሬት ለቡድኑ አባላት በስም አዙሯል።
🎖️ የክብር ማዕረግ፦
ከገንዘብ እና ከመሬት ስጦታው ባለፈ፣ ፕሬዝዳንቱ ለታሪካዊው ድል ባለቤቶች የሀገሪቱን ከፍተኛ የክብር "የኮማንደር ማዕረግ" (National Order of the Lion) ሰጥተዋል።
በድምሩ የሴኔጋል መንግስት ከ 6.2 ሚሊዮን ዶላር በላይ ለዚህ ድል ወጪ ማድረጉ ታውቋል። ይህ እርምጃ ሀገሪቱ ለስፖርቱ ያላትን ትልቅ ክብር እና ለወጣቶቿ የምትሰጠውን ማበረታቻ በግልጽ ያሳየ ሆኗል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#senegal #africanchampions #bassiroudiomayefaye #terangalions #footballnews #africacup #inspiration #ethiopia
4 months ago
🏆በዋንጫ ድርቅ የተመቱ ሀገራት ሪከርድን ኢትዮጵያ ይዛለች
35ኛው የሞሮኮው የአፍሪካ ዋንጫን ሴኔጋል ለሁለተኛ ጊዜ ያሸነፈችበት ታሪክ በማፃፍ ፋይሉ ተዘግቷል።ሞሮኮም ከ50 ዓመታት ትዕግስትና ቆይታ በኃላ ዋንጫውን ለመሳም የነበራት ህልሟም ተጨናግፏል።
ሞሮኮ ለተጨማሪ ዓመታት በዋንጫ ድርቅ እንደተጠቃች እንድትቀጥል የሴኔጋል አሸናፊነት ፈርዶባታል።ለመሆኑ ዋንጫውን ካነሱ በኃላ ድጋሚ ከፍ አድርጎ ለማንሳት ዕድል በማጣታቸው በዋንጫ ድርቅ ተጠቅተው ዓመታትን በማስቆጠር ላይ የሚገኙ ሀገራትን ሪከርድ የአፍሪካ ዋንጫ መስራቿ ሀገር ኢትዮጵያ እንደያዘቸው ከዚህ በታች ያለው የቁጥር መረጃ ይነግረናል።
ኢትዮጵያ የአፍሪካ ዋንጫን ካነሳች ድፍን 64 ዓመታትን አስቆጥራ በደካማ ታሪክ እየመራች ነው ይለናል፤ይሄንን ደካማ የውጤት ታሪካችንን የሚቀይረው ትውልድ መቼ ይሆን የሚፈጠረው?
✍️✍️በጋዜጠኛ ይስሀቅ በላይ(ሀትሪክ ስፖርት ኦፊሺያል)
35ኛው የሞሮኮው የአፍሪካ ዋንጫን ሴኔጋል ለሁለተኛ ጊዜ ያሸነፈችበት ታሪክ በማፃፍ ፋይሉ ተዘግቷል።ሞሮኮም ከ50 ዓመታት ትዕግስትና ቆይታ በኃላ ዋንጫውን ለመሳም የነበራት ህልሟም ተጨናግፏል።
ሞሮኮ ለተጨማሪ ዓመታት በዋንጫ ድርቅ እንደተጠቃች እንድትቀጥል የሴኔጋል አሸናፊነት ፈርዶባታል።ለመሆኑ ዋንጫውን ካነሱ በኃላ ድጋሚ ከፍ አድርጎ ለማንሳት ዕድል በማጣታቸው በዋንጫ ድርቅ ተጠቅተው ዓመታትን በማስቆጠር ላይ የሚገኙ ሀገራትን ሪከርድ የአፍሪካ ዋንጫ መስራቿ ሀገር ኢትዮጵያ እንደያዘቸው ከዚህ በታች ያለው የቁጥር መረጃ ይነግረናል።
ኢትዮጵያ የአፍሪካ ዋንጫን ካነሳች ድፍን 64 ዓመታትን አስቆጥራ በደካማ ታሪክ እየመራች ነው ይለናል፤ይሄንን ደካማ የውጤት ታሪካችንን የሚቀይረው ትውልድ መቼ ይሆን የሚፈጠረው?
✍️✍️በጋዜጠኛ ይስሀቅ በላይ(ሀትሪክ ስፖርት ኦፊሺያል)
Sponsored by
Surafel
4 months ago
ከእንባ ወደ ድል፡ የቴራንጋ አንበሶች የክብር ጉዞ
በምዕራብ አፍሪካዊቷ ሀገር ሴኔጋል፣ ዳካር ከተማ ውስጥ የፀሐይ ግርማ ሞገስ በደመቀበት በዚያ ረፋድ ላይ፣ የከተማዋ አየር በከባድ የደስታ ጩኸት፣ በቩቩዜላ ድምፅ እና በኩራት እንባ ተሞልቷል። ይህ ተራ የድል በዓል አልነበረም፤ ይህ በስቃይ፣ በፖለቲካዊ አለመረጋጋት እና በኢኮኖሚ ፈተናዎች ውስጥ ለቆየ ህዝብ የአዲስ ተስፋ ትንሳኤ ነበር።
የሴኔጋል ብሔራዊ ቡድን በሞሮኮ መሬት ላይ አስተናጋጇን ሞሮኮን 1 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸንፎ የአፍሪካ ዋንጫን ለሁለተኛ ጊዜ ይዞ ሲመለስ፣ መላው የሀገሪቱ ህዝብ ስፖርት ከኳስ ጨዋነት ባለፈ እንዴት የቆሰለ ልብን እንደሚፈውስ በተግባር የታየበት ታሪካዊ አጋጣሚ ነበር።
የሰቆቃው ማግስት እና የተስፋው ጭላንጭል
ሴኔጋል ላለፉት ጥቂት ዓመታት (2021-2024) በከባድ የፖለቲካ ውጥረት ውስጥ ነበረች። በጎዳናዎች ላይ ደም ፈሷል፣ በደርዘን የሚቆጠሩ ወጣቶች ህይወታቸውን አጥተዋል፣ ቤተሰቦች ተበታትነዋል፣ እናም ማህበራዊ ትስስሩ አደጋ ላይ ወድቆ ነበር።
ኢኮኖሚያዊ ጫናው ደግሞ በየቤቱ የሚያንኳኳ የዕለት ተዕለት ጭንቀት ሆኖ ቆይቷል።
ይሁን እንጂ በረባቱ ፍጻሜ ጨዋታ ላይ ሳዲዮ ማኔ እና ጓደኞቹ ወደ ሜዳ ሲገቡ፣ በዳካርም ሆነ በካፍሪን ያሉ ህዝቦች የፖለቲካ ልዩነታቸውን፣ የሃይማኖት ልዩነታቸውን እና የግል ችግራቸውን በደጃፋቸው ላይ ጥለው ነበር የወጡት። ፓፔ ጉዬ በጭማሪ ሰዓት ያገባት ያቺ ብቸኛ ጎል፣ ለሴኔጋል ህዝብ ጎል ብቻ አልነበረችም፤ የነፃነት፣ የአንድነት እና የድል አዋጅ እንጂ።
የዳካር ጎዳናዎች ምስክርነት
አንበሶቹ ከሞሮኮ ተመልሰው ዳካር ሲገቡ የነበረው ትዕይንት ለሚያይ ሰው ልብን የሚነካ ነበር። በሺዎች የሚቆጠሩ ደጋፊዎች የአውቶቡሱን መንገድ አጥለቅልቀውታል። አንዳንዶች በህንፃዎች ላይ ተሰቅለዋል፣ ሌሎች በማስታወቂያ ሰሌዳዎች ላይ ተንጠልጥለዋል፤ ሁሉም አንድ ዓላማ ብቻ አላቸው—ጀግኖቻቸውን በአይን ማየት።
አንድ እድሜያቸው በሰላሳዎቹ ውስጥ የሚገኝ "ሆርተንስ ኬኒ" የተባሉ እናት፣ የአምስት ዓመት ልጃቸውን አቅፈው በፓቴ ዲኦይ አውራ ጎዳና ላይ ቆመው በደስታ ሲያለቅሱ ታይተዋል። "አንበሶቹ መላውን ህዝብ ኩሩ አድርገውታል" ሲሉ ተናግረዋል። ይህ ንግግር ከአንድ ስፖርት ወዳጅ የሚወጣ ብቻ ሳይሆን፣ ባለፉት ዓመታት ለደረሰባቸው ሰቆቃ ማስታገሻ ያገኙ እናት ምስክርነት ነበር።
ሳዲዮ ማኔ፣ የአውቶቡሱ ጣሪያ ላይ ሆኖ ዋንጫውን ወደ ሰማይ ከፍ ሲያደርግ፣ ከታች ያለው ህዝብ እንደ ባህር ሞገድ ሲወዛወዝ ይታይ ነበር። ማኔ ለሴኔጋላውያን ተጫዋች ብቻ አይደለም፤ እሱ የትዕግስት፣ የትህትና እና ለሀገር የመኖር ተምሳሌት ነው። በጨዋታው ላይ የነበረው ጫና፣ የዳኞች ውሳኔ እና የደጋፊዎች ጩኸት ሳይበግረው ቡድኑን በብስለት መምራቱ የሀገሪቱን ታሪክ ቀይሮታል።
የአንድነት ጥሪ እና የሪፐብሊካዊ መንፈስ
ይህ ድል ስፖርታዊ ብቻ ሳይሆን ፖለቲካዊ እርቅንም ያመጣል የሚል ተስፋ አለ። ፕሬዝዳንት ባሲሩ ዲዮማይ ፋዬ ተጫዋቾቹን "ሀገር ወዳዶች" ሲሉ በታላቅ ክብር ጠርተዋቸዋል። የፖለቲካ ተቃዋሚዎች ሳይቀሩ፣ ለምሳሌ ቲዬርኖ ቦኩም፣ በፕሬዝዳንቱ ግብዣ መሰረት በቤተመንግስት በተዘጋጀው የክብር አቀባበል ላይ ለመገኘት ወስነዋል። "ይህ ቅጽበት ከስፖርት በላይ ነው፤ ይህ የብሔራዊ አንድነታችን መገለጫ ነው" ሲሉ መናገራቸው፣ ኳስ እንዴት የፖለቲካ ቁስልን እንደምትጠግን ትልቅ ማሳያ ነው።
በካፍሪን ከተማ ደግሞ ሁኔታው የበለጠ ስሜታዊ ነበር። ደጋፊዎች በጃካርታ ሞተር ብስክሌቶች፣ በእግር እና በመኪናዎች ከተማዋን አጥለቅልቀዋታል። ድሉ ከተገኘ በኋላ የነበረው የጭፈራ እና የዝማሬ መንፈስ፣ ለዓመታት በዝምታ እና በጭንቀት ውስጥ የነበረን ህዝብ ነፃ ያወጣ ይመስላል።
ታላቅነት የሚወለደው ከመከራ ነው
የቴራንጋ አንበሶች ጉዞ የሚያስተምረን ትልቅ ቁምነገር አለ፡- እውነተኛ ታላቅነት የሚገነባው በምቾት ጊዜ ሳይሆን በመከራ ውስጥ ነው። ሴኔጋል የገጠማት ፈተናዎች፣ በሜዳ ላይ የነበረው ከባድ ፉክክር እና የመላው ህዝብ ጫና ተዳምሮ ተጫዋቾቹን ወደ ብረትነት ቀይሯቸዋል።
እነሱ ለራሳቸው አልተጫወቱም፤ እነሱ የተጫወቱት በዳካር ጎዳና ጫማ ለሌላቸው ህፃናት፣ ልጆቻቸውን በረሃብ ለሚያጡ እናቶች እና ተስፋ ለቆረጡ ወጣቶች ነበር።
ያቺ የአፍሪካ ዋንጫ፣ ብረት ብቻ አይደለችም፤ የሴኔጋል ህዝብ እንባ፣ ላብ እና ጽናት ተቀላቅሎ የተሰራ ድንቅ ጥበብ እንጂ። ዛሬ ሴኔጋላውያን ወደ 2026ቱ የዓለም ዋንጫ ሲመለከቱ፣ ከፈረንሳይ ጋር የሚኖራቸውን ጨዋታ በጉጉት ሲጠባበቁ፣ የሚያዩት ተራ የእግር ኳስ ግጥሚያን አይደለም።
የሚያዩት የአፍሪካን ኩራት፣ የጥቁር ህዝብን ጽናት እና "ካልተሰበርን አንሸነፍም" የሚለውን የጀግንነት መዝሙር ነው።
መደምደሚያ
በስተመጨረሻ፣ የቴራንጋ አንበሶች ወደ ቤተመንግስት ሲገቡ እና ፕሬዝዳንቱ ዋንጫውን ሲረከቡ፣ የነበረው ፀጥታና የክብር ስሜት ሴኔጋል ዳግም መወለዷን የሚያበስር ነበር። ስፖርት ሰዎችን የማቀራረብ፣ የማስታረቅ እና ተስፋን የመዝራት ተአምራዊ ኃይል እንዳለው ይህ የሴኔጋል የድል ጉዞ ለዓለም አሳይቷል።
ለሴኔጋል አንበሶች እንኳን ደስ አላችሁ! ለጋለ አቀባበል ላደረገው ለሴኔጋል ህዝብም ክብር ይሁን! ይህ ድል የእናንተ ብቻ ሳይሆን፣ በመከራ ውስጥ ሆኖ ብርሃንን ለሚጠባበቅ ለእያንዳንዱ አፍሪካዊ ትልቅ ትምህርት ነው።
በምዕራብ አፍሪካዊቷ ሀገር ሴኔጋል፣ ዳካር ከተማ ውስጥ የፀሐይ ግርማ ሞገስ በደመቀበት በዚያ ረፋድ ላይ፣ የከተማዋ አየር በከባድ የደስታ ጩኸት፣ በቩቩዜላ ድምፅ እና በኩራት እንባ ተሞልቷል። ይህ ተራ የድል በዓል አልነበረም፤ ይህ በስቃይ፣ በፖለቲካዊ አለመረጋጋት እና በኢኮኖሚ ፈተናዎች ውስጥ ለቆየ ህዝብ የአዲስ ተስፋ ትንሳኤ ነበር።
የሴኔጋል ብሔራዊ ቡድን በሞሮኮ መሬት ላይ አስተናጋጇን ሞሮኮን 1 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸንፎ የአፍሪካ ዋንጫን ለሁለተኛ ጊዜ ይዞ ሲመለስ፣ መላው የሀገሪቱ ህዝብ ስፖርት ከኳስ ጨዋነት ባለፈ እንዴት የቆሰለ ልብን እንደሚፈውስ በተግባር የታየበት ታሪካዊ አጋጣሚ ነበር።
የሰቆቃው ማግስት እና የተስፋው ጭላንጭል
ሴኔጋል ላለፉት ጥቂት ዓመታት (2021-2024) በከባድ የፖለቲካ ውጥረት ውስጥ ነበረች። በጎዳናዎች ላይ ደም ፈሷል፣ በደርዘን የሚቆጠሩ ወጣቶች ህይወታቸውን አጥተዋል፣ ቤተሰቦች ተበታትነዋል፣ እናም ማህበራዊ ትስስሩ አደጋ ላይ ወድቆ ነበር።
ኢኮኖሚያዊ ጫናው ደግሞ በየቤቱ የሚያንኳኳ የዕለት ተዕለት ጭንቀት ሆኖ ቆይቷል።
ይሁን እንጂ በረባቱ ፍጻሜ ጨዋታ ላይ ሳዲዮ ማኔ እና ጓደኞቹ ወደ ሜዳ ሲገቡ፣ በዳካርም ሆነ በካፍሪን ያሉ ህዝቦች የፖለቲካ ልዩነታቸውን፣ የሃይማኖት ልዩነታቸውን እና የግል ችግራቸውን በደጃፋቸው ላይ ጥለው ነበር የወጡት። ፓፔ ጉዬ በጭማሪ ሰዓት ያገባት ያቺ ብቸኛ ጎል፣ ለሴኔጋል ህዝብ ጎል ብቻ አልነበረችም፤ የነፃነት፣ የአንድነት እና የድል አዋጅ እንጂ።
የዳካር ጎዳናዎች ምስክርነት
አንበሶቹ ከሞሮኮ ተመልሰው ዳካር ሲገቡ የነበረው ትዕይንት ለሚያይ ሰው ልብን የሚነካ ነበር። በሺዎች የሚቆጠሩ ደጋፊዎች የአውቶቡሱን መንገድ አጥለቅልቀውታል። አንዳንዶች በህንፃዎች ላይ ተሰቅለዋል፣ ሌሎች በማስታወቂያ ሰሌዳዎች ላይ ተንጠልጥለዋል፤ ሁሉም አንድ ዓላማ ብቻ አላቸው—ጀግኖቻቸውን በአይን ማየት።
አንድ እድሜያቸው በሰላሳዎቹ ውስጥ የሚገኝ "ሆርተንስ ኬኒ" የተባሉ እናት፣ የአምስት ዓመት ልጃቸውን አቅፈው በፓቴ ዲኦይ አውራ ጎዳና ላይ ቆመው በደስታ ሲያለቅሱ ታይተዋል። "አንበሶቹ መላውን ህዝብ ኩሩ አድርገውታል" ሲሉ ተናግረዋል። ይህ ንግግር ከአንድ ስፖርት ወዳጅ የሚወጣ ብቻ ሳይሆን፣ ባለፉት ዓመታት ለደረሰባቸው ሰቆቃ ማስታገሻ ያገኙ እናት ምስክርነት ነበር።
ሳዲዮ ማኔ፣ የአውቶቡሱ ጣሪያ ላይ ሆኖ ዋንጫውን ወደ ሰማይ ከፍ ሲያደርግ፣ ከታች ያለው ህዝብ እንደ ባህር ሞገድ ሲወዛወዝ ይታይ ነበር። ማኔ ለሴኔጋላውያን ተጫዋች ብቻ አይደለም፤ እሱ የትዕግስት፣ የትህትና እና ለሀገር የመኖር ተምሳሌት ነው። በጨዋታው ላይ የነበረው ጫና፣ የዳኞች ውሳኔ እና የደጋፊዎች ጩኸት ሳይበግረው ቡድኑን በብስለት መምራቱ የሀገሪቱን ታሪክ ቀይሮታል።
የአንድነት ጥሪ እና የሪፐብሊካዊ መንፈስ
ይህ ድል ስፖርታዊ ብቻ ሳይሆን ፖለቲካዊ እርቅንም ያመጣል የሚል ተስፋ አለ። ፕሬዝዳንት ባሲሩ ዲዮማይ ፋዬ ተጫዋቾቹን "ሀገር ወዳዶች" ሲሉ በታላቅ ክብር ጠርተዋቸዋል። የፖለቲካ ተቃዋሚዎች ሳይቀሩ፣ ለምሳሌ ቲዬርኖ ቦኩም፣ በፕሬዝዳንቱ ግብዣ መሰረት በቤተመንግስት በተዘጋጀው የክብር አቀባበል ላይ ለመገኘት ወስነዋል። "ይህ ቅጽበት ከስፖርት በላይ ነው፤ ይህ የብሔራዊ አንድነታችን መገለጫ ነው" ሲሉ መናገራቸው፣ ኳስ እንዴት የፖለቲካ ቁስልን እንደምትጠግን ትልቅ ማሳያ ነው።
በካፍሪን ከተማ ደግሞ ሁኔታው የበለጠ ስሜታዊ ነበር። ደጋፊዎች በጃካርታ ሞተር ብስክሌቶች፣ በእግር እና በመኪናዎች ከተማዋን አጥለቅልቀዋታል። ድሉ ከተገኘ በኋላ የነበረው የጭፈራ እና የዝማሬ መንፈስ፣ ለዓመታት በዝምታ እና በጭንቀት ውስጥ የነበረን ህዝብ ነፃ ያወጣ ይመስላል።
ታላቅነት የሚወለደው ከመከራ ነው
የቴራንጋ አንበሶች ጉዞ የሚያስተምረን ትልቅ ቁምነገር አለ፡- እውነተኛ ታላቅነት የሚገነባው በምቾት ጊዜ ሳይሆን በመከራ ውስጥ ነው። ሴኔጋል የገጠማት ፈተናዎች፣ በሜዳ ላይ የነበረው ከባድ ፉክክር እና የመላው ህዝብ ጫና ተዳምሮ ተጫዋቾቹን ወደ ብረትነት ቀይሯቸዋል።
እነሱ ለራሳቸው አልተጫወቱም፤ እነሱ የተጫወቱት በዳካር ጎዳና ጫማ ለሌላቸው ህፃናት፣ ልጆቻቸውን በረሃብ ለሚያጡ እናቶች እና ተስፋ ለቆረጡ ወጣቶች ነበር።
ያቺ የአፍሪካ ዋንጫ፣ ብረት ብቻ አይደለችም፤ የሴኔጋል ህዝብ እንባ፣ ላብ እና ጽናት ተቀላቅሎ የተሰራ ድንቅ ጥበብ እንጂ። ዛሬ ሴኔጋላውያን ወደ 2026ቱ የዓለም ዋንጫ ሲመለከቱ፣ ከፈረንሳይ ጋር የሚኖራቸውን ጨዋታ በጉጉት ሲጠባበቁ፣ የሚያዩት ተራ የእግር ኳስ ግጥሚያን አይደለም።
የሚያዩት የአፍሪካን ኩራት፣ የጥቁር ህዝብን ጽናት እና "ካልተሰበርን አንሸነፍም" የሚለውን የጀግንነት መዝሙር ነው።
መደምደሚያ
በስተመጨረሻ፣ የቴራንጋ አንበሶች ወደ ቤተመንግስት ሲገቡ እና ፕሬዝዳንቱ ዋንጫውን ሲረከቡ፣ የነበረው ፀጥታና የክብር ስሜት ሴኔጋል ዳግም መወለዷን የሚያበስር ነበር። ስፖርት ሰዎችን የማቀራረብ፣ የማስታረቅ እና ተስፋን የመዝራት ተአምራዊ ኃይል እንዳለው ይህ የሴኔጋል የድል ጉዞ ለዓለም አሳይቷል።
ለሴኔጋል አንበሶች እንኳን ደስ አላችሁ! ለጋለ አቀባበል ላደረገው ለሴኔጋል ህዝብም ክብር ይሁን! ይህ ድል የእናንተ ብቻ ሳይሆን፣ በመከራ ውስጥ ሆኖ ብርሃንን ለሚጠባበቅ ለእያንዳንዱ አፍሪካዊ ትልቅ ትምህርት ነው።
5 months ago
በሞሮኮ የ27 ዓመት ሴኔጋላዊ ወጣት ትላንት ምሽት በቢላዋ ጥቃት መገደሉ ተሰማ
#ethiopia | ይህ ግድያ በሞሮኮ እና በሴኔጋል መካከል ያለውን ዲፕሎማሲያዊና ስፖርታዊ ግንኙነት ወደ ከባድ ውጥረት ውስጥ ከቶታል።
እንደ ሴኔጋል መገናኛ ብዙሃን ዘገባ፣ ጥቃቱ የተፈጸመው ሞሮኮ በአፍሪካ ዋንጫ (AFCON 2025) በሴኔጋል መሸነፏን ተከትሎ በደጋፊዎች መካከል ከፍተኛ አለመግባባት በነገሰበት ወቅት ነው።
የክስተቱ ዝርዝር ሁኔታ፦
* ጥቃቱ፦ ወጣቱ ሼክ ዲዩፍ በካዛብላንካ ጎዳናዎች ላይ በቡድን በታጠቁ ሰዎች ተከቦ በደረሰበት የስለት ጥቃት ሕይወቱ አልፏል።
* የፖሊስ እርምጃ፦ የሞሮኮ የፀጥታ አካላት በወንጀሉ የተጠረጠሩ ግለሰቦችን በቁጥጥር ስር ማዋላቸውን ገልጸዋል። ሆኖም የግድያው መነሻ "የስፖርት ደጋፊዎች ግጭት" ይሁን ወይም "ዘረኝነት" (Racism) በሚለው ላይ ጥልቅ ምርመራ እያደረጉ መሆኑን አስታውቀዋል።
* ዲፕሎማሲያዊ ማስጠንቀቂያ፦ በሞሮኮ የሚገኘው የሴኔጋል ኤምባሲ በጉዳዩ ላይ ያለውን ስጋት ገልጾ፣ በሀገሪቱ የሚኖሩ ዜጎቹ ከፍተኛ ጥንቃቄ እንዲያደርጉና በተለይም በምሽት እንቅስቃሴያቸውን እንዲገድቡ አሳስቧል።
የማህበራዊ ሚዲያ ቁጣ፦
ይህ ድርጊት በአህጉሪቱ በሚገኙ አፍሪካውያን ዘንድ ከፍተኛ ቁጣን ቀስቅሷል። በማህበራዊ ሚዲያ መድረኮች ላይ #justiceforcheikhdiouf በሚል መሪ ቃል ወንጀለኞች ተገቢውን ቅጣት እንዲያገኙና በአፍሪካውያን ላይ የሚፈጸም የዘረኝነት ጥቃት እንዲቆም የሚጠይቁ ዘመቻዎች በስፋት እየተሰራጩ ይገኛሉ።
ይህ ክስተት ስፖርት አንድነትን ከመፍጠር ይልቅ ለግጭትና ለጥላቻ መነሻ እንዳይሆን ስጋት የፈጠረ ሲሆን፣ የሁለቱ ሀገራት መንግስታት ሁኔታውን ለማረጋጋት ምን እርምጃ ይወስዳሉ የሚለው በጉጉት እየተጠበቀ ነው።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#justiceforcheikhdiouf #senegal #morocco #afcon2025 #stopracism #casablanca #africaunited #breakingnews #የአፍሪካዜና #ፍትህለሼክዲዩፍ
#ethiopia | ይህ ግድያ በሞሮኮ እና በሴኔጋል መካከል ያለውን ዲፕሎማሲያዊና ስፖርታዊ ግንኙነት ወደ ከባድ ውጥረት ውስጥ ከቶታል።
እንደ ሴኔጋል መገናኛ ብዙሃን ዘገባ፣ ጥቃቱ የተፈጸመው ሞሮኮ በአፍሪካ ዋንጫ (AFCON 2025) በሴኔጋል መሸነፏን ተከትሎ በደጋፊዎች መካከል ከፍተኛ አለመግባባት በነገሰበት ወቅት ነው።
የክስተቱ ዝርዝር ሁኔታ፦
* ጥቃቱ፦ ወጣቱ ሼክ ዲዩፍ በካዛብላንካ ጎዳናዎች ላይ በቡድን በታጠቁ ሰዎች ተከቦ በደረሰበት የስለት ጥቃት ሕይወቱ አልፏል።
* የፖሊስ እርምጃ፦ የሞሮኮ የፀጥታ አካላት በወንጀሉ የተጠረጠሩ ግለሰቦችን በቁጥጥር ስር ማዋላቸውን ገልጸዋል። ሆኖም የግድያው መነሻ "የስፖርት ደጋፊዎች ግጭት" ይሁን ወይም "ዘረኝነት" (Racism) በሚለው ላይ ጥልቅ ምርመራ እያደረጉ መሆኑን አስታውቀዋል።
* ዲፕሎማሲያዊ ማስጠንቀቂያ፦ በሞሮኮ የሚገኘው የሴኔጋል ኤምባሲ በጉዳዩ ላይ ያለውን ስጋት ገልጾ፣ በሀገሪቱ የሚኖሩ ዜጎቹ ከፍተኛ ጥንቃቄ እንዲያደርጉና በተለይም በምሽት እንቅስቃሴያቸውን እንዲገድቡ አሳስቧል።
የማህበራዊ ሚዲያ ቁጣ፦
ይህ ድርጊት በአህጉሪቱ በሚገኙ አፍሪካውያን ዘንድ ከፍተኛ ቁጣን ቀስቅሷል። በማህበራዊ ሚዲያ መድረኮች ላይ #justiceforcheikhdiouf በሚል መሪ ቃል ወንጀለኞች ተገቢውን ቅጣት እንዲያገኙና በአፍሪካውያን ላይ የሚፈጸም የዘረኝነት ጥቃት እንዲቆም የሚጠይቁ ዘመቻዎች በስፋት እየተሰራጩ ይገኛሉ።
ይህ ክስተት ስፖርት አንድነትን ከመፍጠር ይልቅ ለግጭትና ለጥላቻ መነሻ እንዳይሆን ስጋት የፈጠረ ሲሆን፣ የሁለቱ ሀገራት መንግስታት ሁኔታውን ለማረጋጋት ምን እርምጃ ይወስዳሉ የሚለው በጉጉት እየተጠበቀ ነው።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#justiceforcheikhdiouf #senegal #morocco #afcon2025 #stopracism #casablanca #africaunited #breakingnews #የአፍሪካዜና #ፍትህለሼክዲዩፍ
5 months ago
በሞሮኮ የሴኔጋል ዜጋ በጭካኔ ተገደለ
በሞሮኮ ካዛብላንካ ከተማ ሼክ ዲዩፍ የተባለ የ27 ዓመት ሴኔጋላዊ ወጣት በስለት ተወግቶ መገደሉ የሴኔጋል መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል።
ዝርዝር መረጃዎች፦
• የግድያው ሁኔታ፦ ሼክ ዲዩፍ የተገደለው ትላንት ምሽት በካዛብላንካ መንገዶች ላይ በቡድን በደረሰበት ጥቃት እንደሆነ ተዘግቧል።
• ከእግር ኳስ ጋር ያለው ግንኙነት፦ ግድያው የተፈጸመው ሞሮኮ በአፍሪካ ዋንጫ (AFCON 2025) በሴኔጋል መሸነፏን ተከትሎ በሁለቱ ሀገራት ደጋፊዎች መካከል ከፍተኛ ውጥረት በነገሰበት ወቅት ነው።
• የፖሊስ ምርመራ፦ የሞሮኮ ፖሊስ ወንጀሉን የፈጸሙ ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር ማዋሉን ቢገልጽም፣ የግድያው ትክክለኛ መንስኤ "ዘረኝነት" ይሁን ወይም "የስፖርት ደጋፊዎች ግጭት" በሚለው ላይ ምርመራው ቀጥሏል።
• የሴኔጋል መንግስት ምላሽ፦ በሞሮኮ የሚገኘው የሴኔጋል ኤምባሲ ለዜጎቹ ከፍተኛ ጥንቃቄ እንዲያደርጉና በምሽት ከቤት እንዳይወጡ ማስጠንቀቂያ አስተላልፏል።
ይህ ድርጊት በበርካታ አፍሪካውያን ዘንድ ከፍተኛ ቁጣን የቀሰቀሰ ሲሆን፣ በማህበራዊ ሚዲያ ላይ #justiceforcheikhdiouf የሚል ዘመቻ ተጀምሯል።
በሞሮኮ ካዛብላንካ ከተማ ሼክ ዲዩፍ የተባለ የ27 ዓመት ሴኔጋላዊ ወጣት በስለት ተወግቶ መገደሉ የሴኔጋል መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል።
ዝርዝር መረጃዎች፦
• የግድያው ሁኔታ፦ ሼክ ዲዩፍ የተገደለው ትላንት ምሽት በካዛብላንካ መንገዶች ላይ በቡድን በደረሰበት ጥቃት እንደሆነ ተዘግቧል።
• ከእግር ኳስ ጋር ያለው ግንኙነት፦ ግድያው የተፈጸመው ሞሮኮ በአፍሪካ ዋንጫ (AFCON 2025) በሴኔጋል መሸነፏን ተከትሎ በሁለቱ ሀገራት ደጋፊዎች መካከል ከፍተኛ ውጥረት በነገሰበት ወቅት ነው።
• የፖሊስ ምርመራ፦ የሞሮኮ ፖሊስ ወንጀሉን የፈጸሙ ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር ማዋሉን ቢገልጽም፣ የግድያው ትክክለኛ መንስኤ "ዘረኝነት" ይሁን ወይም "የስፖርት ደጋፊዎች ግጭት" በሚለው ላይ ምርመራው ቀጥሏል።
• የሴኔጋል መንግስት ምላሽ፦ በሞሮኮ የሚገኘው የሴኔጋል ኤምባሲ ለዜጎቹ ከፍተኛ ጥንቃቄ እንዲያደርጉና በምሽት ከቤት እንዳይወጡ ማስጠንቀቂያ አስተላልፏል።
ይህ ድርጊት በበርካታ አፍሪካውያን ዘንድ ከፍተኛ ቁጣን የቀሰቀሰ ሲሆን፣ በማህበራዊ ሚዲያ ላይ #justiceforcheikhdiouf የሚል ዘመቻ ተጀምሯል።
5 months ago
የሴኔጋል ብሔራዊ ቡድን ዋና አሰልጣኝ ፓፔ ቲያው ተገዱ
#ethiopia | የሴኔጋል ብሔራዊ ቡድን ዋና አሰልጣኝ ፓፔ ቲያው በአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን (ካፍ) ላልተወሰነ ጊዜ ከእግር ኳስ እንቅስቃሴ ታገዱ።
ይህ እገዳ የመጣው በ2025 የአፍሪካ ዋንጫ ፍጻሜ ጨዋታ ከአዘጋጇ ሞሮኮ ጋር ሲጫወቱ፣ ዳኛው የወሰኑትን አወዛጋቢ ውሳኔ በመቃወም ተጫዋቾቻቸው ሜዳውን ለቀው እንዲወጡ በማዘዛቸው ምክንያት ነው።
የሴኔጋሉ አሰልጣኝ ባደረጉት ድርጊት መጸጸታቸውን በመግለጽ ይቅርታ ጠይቀዋል።
በሌላ በኩል፣ ከካፍ በኩል ስለ እገዳው ዝርዝር ሁኔታ ተጨማሪ መረጃ እየተጠበቀ ነው።
ለመሆኑ እናንተ ይህን እገዳ እንዴት አያችሁት?
ትክክለኛ ውሳኔ ነው?
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#ሴኔጋል #ሞሮኮ #ካፍ #afcon2025
#ethiopia | የሴኔጋል ብሔራዊ ቡድን ዋና አሰልጣኝ ፓፔ ቲያው በአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን (ካፍ) ላልተወሰነ ጊዜ ከእግር ኳስ እንቅስቃሴ ታገዱ።
ይህ እገዳ የመጣው በ2025 የአፍሪካ ዋንጫ ፍጻሜ ጨዋታ ከአዘጋጇ ሞሮኮ ጋር ሲጫወቱ፣ ዳኛው የወሰኑትን አወዛጋቢ ውሳኔ በመቃወም ተጫዋቾቻቸው ሜዳውን ለቀው እንዲወጡ በማዘዛቸው ምክንያት ነው።
የሴኔጋሉ አሰልጣኝ ባደረጉት ድርጊት መጸጸታቸውን በመግለጽ ይቅርታ ጠይቀዋል።
በሌላ በኩል፣ ከካፍ በኩል ስለ እገዳው ዝርዝር ሁኔታ ተጨማሪ መረጃ እየተጠበቀ ነው።
ለመሆኑ እናንተ ይህን እገዳ እንዴት አያችሁት?
ትክክለኛ ውሳኔ ነው?
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#ሴኔጋል #ሞሮኮ #ካፍ #afcon2025
5 months ago
ሞሮኮ በሴኔጋል ላይ ክስ መሰረተች!
በ2025 የአፍሪካ ዋንጫ (AFCON) የፍጻሜ ጨዋታ ላይ ሴኔጋል ሜዳ ጥላ መውጣቷን ተከትሎ የሞሮኮ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ጉዳዩን ወደ CAF እና FIFA በመውሰድ የህግ እርምጃ እንደሚጀምር አስታውቋል።
ምን ተፈጠረ?
ትላንት እሁድ ጥር 10/2018 ዓ.ም በተካሄደው የፍጻሜ ጨዋታ፣ በመደበኛው የጨዋታ ክፍለ ጊዜ መጠናቀቂያ ላይ ለሞሮኮ የፍጹም ቅጣት ምት ተሰጥቶ ነበር። በዚህ ውሳኔ የተቆጡት የሴኔጋል ተጫዋቾች በቴክኒክ ዳይሬክተራቸው ፓፔ ቲያው ትዕዛዝ ለ15 ደቂቃ ያህል ሜዳ ጥለው ወጥተው ነበር።
የሞሮኮ ቅሬታ፦
የሞሮኮ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ባወጣው መግለጫ፦
❌ የሴኔጋል ተጫዋቾች ሜዳ ጥለው መውጣታቸው በጨዋታው ሂደት እና በተጫዋቾች ስነ-ልቦና ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ አሳድሯል።
❌ ዳኛው የሰጡት የፍጹም ቅጣት ምት ትክክል ሆኖ ሳለ፣ የሴኔጋል ድርጊት ግን ስፖርታዊ ጨዋነት የጎደለውና ህግ የጣሰ ነው።
የጨዋታው ውጤት፦
ሴኔጋል ወደ ሜዳ ተመልሳ ብራሂም ዲያዝ የፍጹም ቅጣት ምቱን ስቶታል። ጨዋታው ወደ ተጨማሪ ሰዓት አምርቶ ሴኔጋል በፓፔ ጉዬ ግብ 1 ለ 0 በማሸነፍ ለሁለተኛ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫን ብታነሳም፣ ጉዳዩ አሁን ወደ ህግ መድረኩ ተሻግሯል።
ካፍ (CAF) በጉዳዩ ላይ ምርመራ መጀመሩን የገለጸ ሲሆን፣ የሴኔጋል አሰልጣኝ በድርጊታቸው ይቅርታ ጠይቀዋል።
በ2025 የአፍሪካ ዋንጫ (AFCON) የፍጻሜ ጨዋታ ላይ ሴኔጋል ሜዳ ጥላ መውጣቷን ተከትሎ የሞሮኮ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ጉዳዩን ወደ CAF እና FIFA በመውሰድ የህግ እርምጃ እንደሚጀምር አስታውቋል።
ምን ተፈጠረ?
ትላንት እሁድ ጥር 10/2018 ዓ.ም በተካሄደው የፍጻሜ ጨዋታ፣ በመደበኛው የጨዋታ ክፍለ ጊዜ መጠናቀቂያ ላይ ለሞሮኮ የፍጹም ቅጣት ምት ተሰጥቶ ነበር። በዚህ ውሳኔ የተቆጡት የሴኔጋል ተጫዋቾች በቴክኒክ ዳይሬክተራቸው ፓፔ ቲያው ትዕዛዝ ለ15 ደቂቃ ያህል ሜዳ ጥለው ወጥተው ነበር።
የሞሮኮ ቅሬታ፦
የሞሮኮ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ባወጣው መግለጫ፦
❌ የሴኔጋል ተጫዋቾች ሜዳ ጥለው መውጣታቸው በጨዋታው ሂደት እና በተጫዋቾች ስነ-ልቦና ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ አሳድሯል።
❌ ዳኛው የሰጡት የፍጹም ቅጣት ምት ትክክል ሆኖ ሳለ፣ የሴኔጋል ድርጊት ግን ስፖርታዊ ጨዋነት የጎደለውና ህግ የጣሰ ነው።
የጨዋታው ውጤት፦
ሴኔጋል ወደ ሜዳ ተመልሳ ብራሂም ዲያዝ የፍጹም ቅጣት ምቱን ስቶታል። ጨዋታው ወደ ተጨማሪ ሰዓት አምርቶ ሴኔጋል በፓፔ ጉዬ ግብ 1 ለ 0 በማሸነፍ ለሁለተኛ ጊዜ የአፍሪካ ዋንጫን ብታነሳም፣ ጉዳዩ አሁን ወደ ህግ መድረኩ ተሻግሯል።
ካፍ (CAF) በጉዳዩ ላይ ምርመራ መጀመሩን የገለጸ ሲሆን፣ የሴኔጋል አሰልጣኝ በድርጊታቸው ይቅርታ ጠይቀዋል።