3 months ago
#update
" የሟቾች ቁጥር 107 ደርሷል " - የጋሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ደምሴ አድማሱ (ዶ/ር)
⚫ " ከአንድ ወረዳ ብቻ 102 ሰዎች ሕይወት ሲያልፍ የ50 ሰዎችን አስክሬን ማግኘት አልተቻለም። "
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጋሞ ዞን ጋጮ ባባ ፣ካምባ እና ቦንኬ ወረዳዎች በደረሰው የመሬት መንሸራተት እና የጎርፍ አደጋ የሟቾች ቁጥር ወደ 107 መድረሱን የጋሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ደምሴ አድማሱ (ዶ/ር) ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
ከሟቾቹ መካከል ከጋጮ ባባ ወረዳ ብቻ 102፣ ከካምባ ወረዳ 2 እንዲሁም ከቦንኬ ወረዳ 3 በድምሩ የ107 ሰዎች ሕይወት ማለፉን አስረድተዋል።
ደምሴ (ዶ/ር) እስካሁን በተከናወነው አስቸጋሪ ፍለጋ የ57 ሰዎች አስክሬን መገኘቱንና በጋጮ ባባ ወረዳ የቀሪ 50 ሰዎች አስክሬን እየተፈለገ መሆኑን ገልፀዋል።
የአከባቢው መልካምድር አስቸጋሪ መሆን አስክሬን ፍለጋውን ከባድ ማድረጉን የገለፁት የዞኑ አስተዳዳሪው ጉዳት ለደረሰባቸውና ለተፈናቀሉ ወገኖች አስቸኳይ የዕለት እርዳት እየተደረገ መሆኑን አስረድተዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ እየተከታተለ ተጨማሪ መረጃ የምያደርስ ይሆናል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሀዋሳ
#tikvahethiopiafamilyhawassa
tikvahethiopia
" የሟቾች ቁጥር 107 ደርሷል " - የጋሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ደምሴ አድማሱ (ዶ/ር)
⚫ " ከአንድ ወረዳ ብቻ 102 ሰዎች ሕይወት ሲያልፍ የ50 ሰዎችን አስክሬን ማግኘት አልተቻለም። "
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጋሞ ዞን ጋጮ ባባ ፣ካምባ እና ቦንኬ ወረዳዎች በደረሰው የመሬት መንሸራተት እና የጎርፍ አደጋ የሟቾች ቁጥር ወደ 107 መድረሱን የጋሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ደምሴ አድማሱ (ዶ/ር) ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
ከሟቾቹ መካከል ከጋጮ ባባ ወረዳ ብቻ 102፣ ከካምባ ወረዳ 2 እንዲሁም ከቦንኬ ወረዳ 3 በድምሩ የ107 ሰዎች ሕይወት ማለፉን አስረድተዋል።
ደምሴ (ዶ/ር) እስካሁን በተከናወነው አስቸጋሪ ፍለጋ የ57 ሰዎች አስክሬን መገኘቱንና በጋጮ ባባ ወረዳ የቀሪ 50 ሰዎች አስክሬን እየተፈለገ መሆኑን ገልፀዋል።
የአከባቢው መልካምድር አስቸጋሪ መሆን አስክሬን ፍለጋውን ከባድ ማድረጉን የገለፁት የዞኑ አስተዳዳሪው ጉዳት ለደረሰባቸውና ለተፈናቀሉ ወገኖች አስቸኳይ የዕለት እርዳት እየተደረገ መሆኑን አስረድተዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ እየተከታተለ ተጨማሪ መረጃ የምያደርስ ይሆናል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሀዋሳ
#tikvahethiopiafamilyhawassa
tikvahethiopia
5 months ago
ሽጉጥ አውጥቶ በማስፈራራት የአስገድዶ መድፈር ወንጀል የፈጸመው የፖሊስ አባል 16 ዓመት ተፈረደበት።
ዋና ሳጅን አሸናፊ ኡኩሞ በወላይታ ዞን ባይራ ኮሻ ወረዳ የወንጀል ምርመራ ክፍል ኃላፊ ናቸው።
ዋና ሳጅን አሸናፊ ኡኩሞ በፈፀሙት የአስገድዶ መድፈር ወንጀል በ16 አመት ጽኑ እስራት መቀጣታቸውን የወላይታ ሶዶ ፖሊስ መመሪያ አዛዥ ኮማንደር ሀብታሙ አሰፋ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አሳውቀዋል።
የወንጀል ድርጊቱ የተፈፀመዉ በቀን 5/1/2018 ዓ.ም ዕለተ ሰኞ በግምት ከምሽቱ ሁለት ሰዓት ገደማ ነው።
የግል ተበዳይ በሶዶ ከተማ አስተዳደር ወደ አጎቷ ቤት በእግር እየመጣች ባለችበት ዋና ሳጅን አሸናፊ " በሞተር ልሸኝሽ " በማለት ካሳፈራት በኋላ ፔንስዮን ይዟት ይገባል።
በኃላም ሽጉጥ አዉጥቶ በማስፈራራት አስገድዶ መድፈሩን በፖሊስ ምርመራና በዐቃቤ ህግ ተረጋግጧል።
በሶዶ ከተማ አስተዳደር የሚገኘዉ የአራዳ ሴቶችና ህጻናት ልዩ ችሎት በተከሳሽ ላይ የቀረበውን ክስ ጥፋተኛ ነው ሲል በ16 ዓመት ፅኑ እስራት እንዲቀጣ ወስኗል።
ከዚሁ የጉዳይ ጋር በተያያዘ በማህበራዊ ሚዲያዎች " ፖሊስ ባልደረባው የሰራውን ወንጀል ለመሸፈን ሞክሯል " የሚሉ ሀሳቦች ሲዘዋወሩ ነበር።
የወላይታ ሶዶ ፖሊስ መመሪያ አዛዥ ኮማንደር ሀብታሙ አሰፋ ግን " ይህ ፍጹም መሰረተ ቢስ እና አግባብነት የሌለው ነው " ብለዋል።
" አንዳንድ ጥላቻ የሚሰብኩ ሚዲያዎች የግለሰቡን ጥፋትና ወንጀል የመላዉ ፖሊስ ተግባር በማስመሰል ሲያቀርቡም ነበር ይህም መሰረተ ቢስ ነው " ሲሉ ገልጸዋል።
" እንዲህ እያሉ ያሰራጩትን እንጠይቃቸዋለን " ብለዋል።
" ፖሊስ እኮ ግለሰቡን አስሮ የምርመራ መዝገብ ከማደራጀት እስከ የዐቃቤ ሕግ ምስክርና የፖሊስ አባል ሆኖ ይህን አስነዋሪ የወንጀል ድርጊት መፈፀሙን በክስ ማክበጃነት እንዲነሳ የድርሻቸውን ሁሉ ተወጥቷል " ብለዋል።
" ከዚህ ባለፈ የዉሳኔዉን ችሎት በሚዲያ እንዲዘገብ ያደረገው እራሱ ፖሊስ ነው ይህ በሆነበት የተቋሙን ገፅታ ለማበላሸት የሚጥሩ አካላት ከድርጊታቸው መታቀብ አለባቸው " ሲሉ አሳስበዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሀዋሳ
#tikvahethiopiafamilyhawassa
tikvahethiopia
ዋና ሳጅን አሸናፊ ኡኩሞ በወላይታ ዞን ባይራ ኮሻ ወረዳ የወንጀል ምርመራ ክፍል ኃላፊ ናቸው።
ዋና ሳጅን አሸናፊ ኡኩሞ በፈፀሙት የአስገድዶ መድፈር ወንጀል በ16 አመት ጽኑ እስራት መቀጣታቸውን የወላይታ ሶዶ ፖሊስ መመሪያ አዛዥ ኮማንደር ሀብታሙ አሰፋ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አሳውቀዋል።
የወንጀል ድርጊቱ የተፈፀመዉ በቀን 5/1/2018 ዓ.ም ዕለተ ሰኞ በግምት ከምሽቱ ሁለት ሰዓት ገደማ ነው።
የግል ተበዳይ በሶዶ ከተማ አስተዳደር ወደ አጎቷ ቤት በእግር እየመጣች ባለችበት ዋና ሳጅን አሸናፊ " በሞተር ልሸኝሽ " በማለት ካሳፈራት በኋላ ፔንስዮን ይዟት ይገባል።
በኃላም ሽጉጥ አዉጥቶ በማስፈራራት አስገድዶ መድፈሩን በፖሊስ ምርመራና በዐቃቤ ህግ ተረጋግጧል።
በሶዶ ከተማ አስተዳደር የሚገኘዉ የአራዳ ሴቶችና ህጻናት ልዩ ችሎት በተከሳሽ ላይ የቀረበውን ክስ ጥፋተኛ ነው ሲል በ16 ዓመት ፅኑ እስራት እንዲቀጣ ወስኗል።
ከዚሁ የጉዳይ ጋር በተያያዘ በማህበራዊ ሚዲያዎች " ፖሊስ ባልደረባው የሰራውን ወንጀል ለመሸፈን ሞክሯል " የሚሉ ሀሳቦች ሲዘዋወሩ ነበር።
የወላይታ ሶዶ ፖሊስ መመሪያ አዛዥ ኮማንደር ሀብታሙ አሰፋ ግን " ይህ ፍጹም መሰረተ ቢስ እና አግባብነት የሌለው ነው " ብለዋል።
" አንዳንድ ጥላቻ የሚሰብኩ ሚዲያዎች የግለሰቡን ጥፋትና ወንጀል የመላዉ ፖሊስ ተግባር በማስመሰል ሲያቀርቡም ነበር ይህም መሰረተ ቢስ ነው " ሲሉ ገልጸዋል።
" እንዲህ እያሉ ያሰራጩትን እንጠይቃቸዋለን " ብለዋል።
" ፖሊስ እኮ ግለሰቡን አስሮ የምርመራ መዝገብ ከማደራጀት እስከ የዐቃቤ ሕግ ምስክርና የፖሊስ አባል ሆኖ ይህን አስነዋሪ የወንጀል ድርጊት መፈፀሙን በክስ ማክበጃነት እንዲነሳ የድርሻቸውን ሁሉ ተወጥቷል " ብለዋል።
" ከዚህ ባለፈ የዉሳኔዉን ችሎት በሚዲያ እንዲዘገብ ያደረገው እራሱ ፖሊስ ነው ይህ በሆነበት የተቋሙን ገፅታ ለማበላሸት የሚጥሩ አካላት ከድርጊታቸው መታቀብ አለባቸው " ሲሉ አሳስበዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሀዋሳ
#tikvahethiopiafamilyhawassa
tikvahethiopia
6 months ago
" እገዳዎች እንዲነሱ ተወስኗል" - የዳሰነች ዘረዳ አስተዳደር
በደቡብ ኦሞ ዞን ዳሰነች ወረዳ አካባቢ በነበረው የማርበርግ ቫይረስ ስርጭት ስጋት ምክንያት በትምህርት ቤቶች፣ የሕዝብ ማመላለሻ ትራንስፖርት አገልግሎትና ሌሎችም ሕዝብ የሚሰበሰብባቸዉ ኩነቶች ላይ ተጥሎ የነበረው በከፊል እንደተነሳ የወረዳው ምክትል አስተዳዳሪ አቶ ኡመር ኖኩዌ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አሳውቀዋል።
በዚሁ መሰረት ፦
- በትምህርት ቤቶች የተማሪዎችን ቁጥር በመቀነስ በፈረቃ ወይንም በማሸጋሸግ እንዲሁም የመከላከያ ዘዴዎችን በማስጠቀም የመማር ማስተማር ስራዉ እንዲቀጥል፤
- የህዝብ ማመላለሻ ትራንስፖርት ባለንብረቶች ከመቼውም ጊዜ በላይ የተሽከርካሪዎችን ንፅህና በሳንታይዘር በመጠበቅ በወንበር ቁጥር ልክ ብቻ እንዲያሳፍሩ፤
- ባለ ሶስት እግር ባጃጆች ከሹፌሩ ውጪ ከሁለት ሰው በላይ መጫን እንደይችሉ፤
- DStv የስፖርት ማዘወትሪያ ስፍራዎች ተጠቃሚዎችን አራርቀው እና የመከላከያ ግባዓቶችን በማስጠቀም አገልግሎት መስጠት እንደሚችሉ ማሻሻያ የተደረገ መሆኑን ገልጸዋል።
ለቅሶ እና ሌሎች ማህበራዊ ጉዳዮች በጥንቃቄ እንዲከወኑ ዉሳኔ ተላልፏል።
በሌላ በኩል የዳሰች አከባቢ ካለዉ ሰፋ ያለ መልክዓ ምድር እና በአንዳንድ ቦታዎች ካለዉ የዉሃ ሙላት መነሻ የማርበርግ ክትባት በድሮን ታግዞ እየተሰራጨ መሆኑን አቶ ኡመር ኖኩዌ ገልጸዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሀዋሳ
#tikvahethiopiafamilyhawassa
tikvahethiopia
በደቡብ ኦሞ ዞን ዳሰነች ወረዳ አካባቢ በነበረው የማርበርግ ቫይረስ ስርጭት ስጋት ምክንያት በትምህርት ቤቶች፣ የሕዝብ ማመላለሻ ትራንስፖርት አገልግሎትና ሌሎችም ሕዝብ የሚሰበሰብባቸዉ ኩነቶች ላይ ተጥሎ የነበረው በከፊል እንደተነሳ የወረዳው ምክትል አስተዳዳሪ አቶ ኡመር ኖኩዌ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አሳውቀዋል።
በዚሁ መሰረት ፦
- በትምህርት ቤቶች የተማሪዎችን ቁጥር በመቀነስ በፈረቃ ወይንም በማሸጋሸግ እንዲሁም የመከላከያ ዘዴዎችን በማስጠቀም የመማር ማስተማር ስራዉ እንዲቀጥል፤
- የህዝብ ማመላለሻ ትራንስፖርት ባለንብረቶች ከመቼውም ጊዜ በላይ የተሽከርካሪዎችን ንፅህና በሳንታይዘር በመጠበቅ በወንበር ቁጥር ልክ ብቻ እንዲያሳፍሩ፤
- ባለ ሶስት እግር ባጃጆች ከሹፌሩ ውጪ ከሁለት ሰው በላይ መጫን እንደይችሉ፤
- DStv የስፖርት ማዘወትሪያ ስፍራዎች ተጠቃሚዎችን አራርቀው እና የመከላከያ ግባዓቶችን በማስጠቀም አገልግሎት መስጠት እንደሚችሉ ማሻሻያ የተደረገ መሆኑን ገልጸዋል።
ለቅሶ እና ሌሎች ማህበራዊ ጉዳዮች በጥንቃቄ እንዲከወኑ ዉሳኔ ተላልፏል።
በሌላ በኩል የዳሰች አከባቢ ካለዉ ሰፋ ያለ መልክዓ ምድር እና በአንዳንድ ቦታዎች ካለዉ የዉሃ ሙላት መነሻ የማርበርግ ክትባት በድሮን ታግዞ እየተሰራጨ መሆኑን አቶ ኡመር ኖኩዌ ገልጸዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሀዋሳ
#tikvahethiopiafamilyhawassa
tikvahethiopia
8 months ago
" የፋይናንስ ባለሙያዎችን ጨምሮ 6 ተጠርጣሪዎች ናቸው በቁጥጥር ስር የዋሉት " - የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ፖሊስ
➡️ " ግለሰቦቹ ቀድሞ ተዘጋጅቶ ቮይድ በተደረገ ቼክ ተመሳሳይ አሳትመዉ ነበር ለማጭበርበር የሞከሩት " - የጎፋ ዞን መንግስት ኮሚኒኬሽን
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል፣ ጎፋ ዞን ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሻቻ ጎዝዲ ቀበሌ ሐምሌ 15 ቀን 2016 ዓ/ም ድንገት ተከስቶ የበርካቶችን ሕይወት የቀጠፈውን የመሬት መንሸራተት አደጋ ተከትሎ የተከሰተውን አጠቃላይ ጉዳት ለማካካስና የተፈናቀሉ ዜጎችን መልሶ ለማቋቋም ድጋፍ ሲሰበሰብ እንደነበር ይታወሳል።
ለተጎጂዎች የተሰበሰበ ከ60 ሚሊዮን ብር በላይ የተወሰኑ ግለሰቦች ተመሳጥረው በተጭበረበረ መንገድ ከባንክ ለማውጣት ሲሞክሩ በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን የሕዝብ ግንኙነት እና ገፅታ ግንባታ ዘርፍ ዳይረክቶሬት ዳይሬክተር ም/ኮማንደር አሸናፊ ሃይለ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
" ገንዘቡን ከፋይናስ ባለሙያዎችና አስተባባሪዎች ጋር በመመሳጠር በአንድ ግለሰብ አማካኝነት በአዲስ አበባ ከተማ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሸገር ቅርንጫፍ ለማስወጣት ሲሞክሩ ባንኩ በሰጠው ጥቆማ መሰረት የደቡብ ኢትዮጵያ ፖሊስ ከአዲስ አበባ ፖሊስ እና የፌዴራል ፖሊስ ጋር በመተባበር ግለሰቡን በቁጥጥር ስር በማዋል ለክልሉ ፖሊስ ተላልፎ ተሰጥቷል " ሲሉ ገልፀዋል።
ከጉዳዩ ጋር ግንኙነት ያላቸዉን የፋይናስ ባለሙያዎችን ጨምሮ 6 ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር መዋላቸዉን ገልፀው በአሁኑ ወቅት ምርመራ እየተደረገባቸው መሆኑንም ተናግረዋል።
የዞኑ መንግስት ምን ይላል ?
የጎፋ ዞን መንግስት 60 ሚሊዮን 276 ሺህ 383 (ስልሳ ሚልዮን ሁለት መቶ ሰባ ስድሰት ሺ ሶስት መቶ ሰማንያ ሶስት ብር ) ቀደም ሲል ተሠርቶ ቮይድ በተደረገ ቼክ ቁጥር ' 42221123 ' ተመሳሳይ በማሳተም ገንዘቡን ለመዝረፍ ካመቻቹ በኋላ ከአዲስ አበባ ንግድ ባንክ ሸገር ቅርንጫፍ ለጎፋ ዞን አስተዳደር በተደረገ ጥቆማ ከአዲስ አበባ እና የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ፖሊስ ጋር በመተባበር ገንዘቡ ሳይወጣ ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን አስታውቋል።
" በተለያዩ ሚዲያዎች ለህብረተሰቡ ትክክለኛና ተጨባጭ መረጃ ከመስጠት ይልቅ ሐሰተኛና የተዛባ መረጃ የሚያሰራጩ የማህበራዊ ሚዲያዎች ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ " ሲል አሳስቧል።
በቀጣይ ከጉዳዩ ጋር በተያያዘ የምርመራው ሂደት ሲጣራ ለሕብረተሰቡ እንደሚያሳውቅ ገልጿል፡፡
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ባደረገው ማጣራት የተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያዎች ገንዘቡን ሲያጭበረብሩ የተያዙት ግለሰቦች የመንግስት የስራ ኃላፊዎች እንደሆኑ የገለፁ ሲሆን ፖሊስ እስካሁን በጉዳዩ ላይ የሰጠዉ መረጃ የለም።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሀዋሳ
#tikvahethiopiafamilyhawassa
tikvahethiopia
➡️ " ግለሰቦቹ ቀድሞ ተዘጋጅቶ ቮይድ በተደረገ ቼክ ተመሳሳይ አሳትመዉ ነበር ለማጭበርበር የሞከሩት " - የጎፋ ዞን መንግስት ኮሚኒኬሽን
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል፣ ጎፋ ዞን ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሻቻ ጎዝዲ ቀበሌ ሐምሌ 15 ቀን 2016 ዓ/ም ድንገት ተከስቶ የበርካቶችን ሕይወት የቀጠፈውን የመሬት መንሸራተት አደጋ ተከትሎ የተከሰተውን አጠቃላይ ጉዳት ለማካካስና የተፈናቀሉ ዜጎችን መልሶ ለማቋቋም ድጋፍ ሲሰበሰብ እንደነበር ይታወሳል።
ለተጎጂዎች የተሰበሰበ ከ60 ሚሊዮን ብር በላይ የተወሰኑ ግለሰቦች ተመሳጥረው በተጭበረበረ መንገድ ከባንክ ለማውጣት ሲሞክሩ በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን የሕዝብ ግንኙነት እና ገፅታ ግንባታ ዘርፍ ዳይረክቶሬት ዳይሬክተር ም/ኮማንደር አሸናፊ ሃይለ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
" ገንዘቡን ከፋይናስ ባለሙያዎችና አስተባባሪዎች ጋር በመመሳጠር በአንድ ግለሰብ አማካኝነት በአዲስ አበባ ከተማ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሸገር ቅርንጫፍ ለማስወጣት ሲሞክሩ ባንኩ በሰጠው ጥቆማ መሰረት የደቡብ ኢትዮጵያ ፖሊስ ከአዲስ አበባ ፖሊስ እና የፌዴራል ፖሊስ ጋር በመተባበር ግለሰቡን በቁጥጥር ስር በማዋል ለክልሉ ፖሊስ ተላልፎ ተሰጥቷል " ሲሉ ገልፀዋል።
ከጉዳዩ ጋር ግንኙነት ያላቸዉን የፋይናስ ባለሙያዎችን ጨምሮ 6 ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር መዋላቸዉን ገልፀው በአሁኑ ወቅት ምርመራ እየተደረገባቸው መሆኑንም ተናግረዋል።
የዞኑ መንግስት ምን ይላል ?
የጎፋ ዞን መንግስት 60 ሚሊዮን 276 ሺህ 383 (ስልሳ ሚልዮን ሁለት መቶ ሰባ ስድሰት ሺ ሶስት መቶ ሰማንያ ሶስት ብር ) ቀደም ሲል ተሠርቶ ቮይድ በተደረገ ቼክ ቁጥር ' 42221123 ' ተመሳሳይ በማሳተም ገንዘቡን ለመዝረፍ ካመቻቹ በኋላ ከአዲስ አበባ ንግድ ባንክ ሸገር ቅርንጫፍ ለጎፋ ዞን አስተዳደር በተደረገ ጥቆማ ከአዲስ አበባ እና የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ፖሊስ ጋር በመተባበር ገንዘቡ ሳይወጣ ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን አስታውቋል።
" በተለያዩ ሚዲያዎች ለህብረተሰቡ ትክክለኛና ተጨባጭ መረጃ ከመስጠት ይልቅ ሐሰተኛና የተዛባ መረጃ የሚያሰራጩ የማህበራዊ ሚዲያዎች ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ " ሲል አሳስቧል።
በቀጣይ ከጉዳዩ ጋር በተያያዘ የምርመራው ሂደት ሲጣራ ለሕብረተሰቡ እንደሚያሳውቅ ገልጿል፡፡
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ባደረገው ማጣራት የተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያዎች ገንዘቡን ሲያጭበረብሩ የተያዙት ግለሰቦች የመንግስት የስራ ኃላፊዎች እንደሆኑ የገለፁ ሲሆን ፖሊስ እስካሁን በጉዳዩ ላይ የሰጠዉ መረጃ የለም።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሀዋሳ
#tikvahethiopiafamilyhawassa
tikvahethiopia
11 months ago
" በአደጋው እስካሁን 4 ሰዎች ህይወታቸው አልፏል " - የሲዳማ ክልል ፖሊስ
➡️ " የወደቁ ተሽከርካሪዎችን በማንሳት መንገድ የማስከፈት ስራ እየተሰራ ነው ! "
ዛሬ በሀዋሳ ከተማ በቱላ ክፍለ ከተማ ' ገመጦ ' ተብሎ በሚጠራው አከባቢ በደረሰ የትራፊክ አደጋ እስካሁን የ4 ሰዎች ህይወት አልፏል።
የሲዳማ ክልል ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ ምክትል ኮሚሽነር የወንጀልና ትራፊክ አደጋ መከላከል ዘርፍ ሀላፊ ረዳት ኮሚሽነር ፍቅሬ ዩእሳ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ እንደተናገሩት ዛሬ ከጠዋቱ 2:30 ገደማ በሀዋሳ ከተማ አስተዳደር በቱላ ክፍለ ከተማ ' ገመጦ ' ተብሎ በሚጠራው አከባቢ በደረሰው የትራፊክ አደጋ 4 ሰዎች ወዲያውኑ ሲሞቱ በሰው እና ንብረት ላይ ጉዳት መድረሱን ገልፀዋል።
አደጋው የደረሰው ወደ ሀዋሳ መስመር ሲጓዝ የነበረ ሲኖትራክ ተሽከርካሪ መስመሩን ስቶ ተሽከርካሪዎችን በመግጨቱ እንዲሁም እግረኞች ላይ በመውጣቱ መሆኑን ገልጸዋል።
በአደጋው በተሽከርካሪው ውስጥ የነበሩ እንዲሁም በእግረኞች ላይ ጉዳት መድረሱን ተናግረዋል።
በአደጋው ምክንያት ጉዳት የደረሰባቸውን ወደ ሀዋሳ ሪፌራል ሆስፒታል የተወሰዱ ሲህን ህብረተሰቡ ከጸጥታ ሀይል ጋር በመተባበር ያደረገው አሰተዋፆ ከፍተኛ መሆኑን አንስተዋል።
በአደጋው ምክንያት ተሽከርካሪዎቹ ዋናዉ መንገድ ላይ በመውደቃቸዉ ምክንያት ዋናዉ መንገድ ዝግ መሆኑንና በክሬን ተሽከርካሪዎችን የማንሳት ስራ እየተሰራ መሆኑን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሀዋሳ
#tikvahethiopiafamilyhawassa
tikvahethiopia
➡️ " የወደቁ ተሽከርካሪዎችን በማንሳት መንገድ የማስከፈት ስራ እየተሰራ ነው ! "
ዛሬ በሀዋሳ ከተማ በቱላ ክፍለ ከተማ ' ገመጦ ' ተብሎ በሚጠራው አከባቢ በደረሰ የትራፊክ አደጋ እስካሁን የ4 ሰዎች ህይወት አልፏል።
የሲዳማ ክልል ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ ምክትል ኮሚሽነር የወንጀልና ትራፊክ አደጋ መከላከል ዘርፍ ሀላፊ ረዳት ኮሚሽነር ፍቅሬ ዩእሳ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ እንደተናገሩት ዛሬ ከጠዋቱ 2:30 ገደማ በሀዋሳ ከተማ አስተዳደር በቱላ ክፍለ ከተማ ' ገመጦ ' ተብሎ በሚጠራው አከባቢ በደረሰው የትራፊክ አደጋ 4 ሰዎች ወዲያውኑ ሲሞቱ በሰው እና ንብረት ላይ ጉዳት መድረሱን ገልፀዋል።
አደጋው የደረሰው ወደ ሀዋሳ መስመር ሲጓዝ የነበረ ሲኖትራክ ተሽከርካሪ መስመሩን ስቶ ተሽከርካሪዎችን በመግጨቱ እንዲሁም እግረኞች ላይ በመውጣቱ መሆኑን ገልጸዋል።
በአደጋው በተሽከርካሪው ውስጥ የነበሩ እንዲሁም በእግረኞች ላይ ጉዳት መድረሱን ተናግረዋል።
በአደጋው ምክንያት ጉዳት የደረሰባቸውን ወደ ሀዋሳ ሪፌራል ሆስፒታል የተወሰዱ ሲህን ህብረተሰቡ ከጸጥታ ሀይል ጋር በመተባበር ያደረገው አሰተዋፆ ከፍተኛ መሆኑን አንስተዋል።
በአደጋው ምክንያት ተሽከርካሪዎቹ ዋናዉ መንገድ ላይ በመውደቃቸዉ ምክንያት ዋናዉ መንገድ ዝግ መሆኑንና በክሬን ተሽከርካሪዎችን የማንሳት ስራ እየተሰራ መሆኑን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሀዋሳ
#tikvahethiopiafamilyhawassa
tikvahethiopia
Comments