Logo
FIDEL POST NEWS
#update

" የሟቾች ቁጥር 107 ደርሷል " - የጋሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ደምሴ አድማሱ (ዶ/ር)

⚫ ‎" ከአንድ ወረዳ ብቻ 102 ሰዎች ሕይወት ሲያልፍ የ50 ሰዎችን አስክሬን ማግኘት አልተቻለም። "

‎በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጋሞ ዞን ጋጮ ባባ ፣ካምባ እና ቦንኬ ወረዳዎች በደረሰው የመሬት መንሸራተት እና የጎርፍ አደጋ የሟቾች ቁጥር ወደ 107 መድረሱን የጋሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ደምሴ አድማሱ (ዶ/ር) ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

‎ከሟቾቹ መካከል ከጋጮ ባባ ወረዳ ብቻ 102፣ ከካምባ ወረዳ 2 እንዲሁም ከቦንኬ ወረዳ 3 በድምሩ የ107 ሰዎች ሕይወት ማለፉን አስረድተዋል።

ደምሴ (ዶ/ር) እስካሁን በተከናወነው አስቸጋሪ ፍለጋ የ57 ሰዎች አስክሬን መገኘቱንና በጋጮ ባባ ወረዳ የቀሪ 50 ሰዎች አስክሬን እየተፈለገ መሆኑን ገልፀዋል።

‎የአከባቢው መልካምድር አስቸጋሪ መሆን አስክሬን ፍለጋውን ከባድ ማድረጉን የገለፁት የዞኑ አስተዳዳሪው ጉዳት ለደረሰባቸውና ለተፈናቀሉ ወገኖች አስቸኳይ የዕለት እርዳት እየተደረገ መሆኑን አስረድተዋል።

‎ቲክቫህ ኢትዮጵያ እየተከታተለ ተጨማሪ መረጃ የምያደርስ ይሆናል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሀዋሳ
#tikvahethiopiafamilyhawassa

tikvahethiopia
3 months ago

No replys yet!

Be the first to share what you think — your comment will appear here.