Logo
Getu Temesgen
የስንዴ ወፍጮ ቤት ሰርተው ልጃቸውን ለቁም ነገር ያበቁ ለዳውን ሲንድረም የተጋለጡ አባት
#ethiopia | ​የዳውን ሲንድረም ያለባቸው ሰዎች ልጅ ማሳደግ አይችሉም የሚለውን የተሳሳተ አመለካከት በመስበር በሶሪያ የሚኖሩት አባት ጃድ ኢሳ ሁሉን የሚያስተምር ታሪክ አስመዝግበዋል።

በስንዴ ወፍጮ ቤት ውስጥ ጠንክረው በመስራት ብቸኛ ልጃቸውን ሳደር ኢሳን በፍቅር፣ በእንክብካቤ እና በሙሉ ድጋፍ ያሳደጉት አባቱ፣ ለልጃቸው የትምህርት ስኬት ትልቅ መሠረት ሆነዋል።

የአባታቱ የማይወላወል ፍቅርና የሥራ ትጋት ብርታት የሆነው ሳደር በትምህርቱ ጠንክሮ በመማር የጥርስ ሐኪም መሆን ችሏል።

የወጣቱ ዶክተር አባት በታላቅ ኩራት "ልጄ ዶክተር ነው" ብለው በየቦታው እንዲናገሩ ሲሆን ፣የጃድና የሳደር ታሪክ እውነተኛ ወላጅነት የሚለካው በፍቅር፣ በመስዋዕትነትና በፅናት እንጂ በቅድመ-ግምት ወይም በጤና ሁኔታ አለመሆኑን ለዓለም ማሳያ ሆኗል።

በያፌት ገ/ህይወት

Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu

1 day ago

No replys yet!

Be the first to share what you think — your comment will appear here.