2 months ago
የሟች ህፃን ናኦድ አጎት የሞት ቅጣት ተላልፈበት
#ethiopia | ላልተገባ ጥቅም ሲባል ህፃን ናኦድ ተኽላይን በአስቃቂ ጭካኔ የገደሉ አራት ወንጀለኞች ከሞት እስከ 23 ዓመት በሚደርስ ፅኑ እስራት ተቀጡ።
ከአራቱ ወንጀለኞች አንዱ በሌለበት የ25 ዓመት ፅኑ እስራት ተፈርዶበታል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ላለፉት ዘጠኝ ወራት ሲከታተለው የቆየው አሰቃቂ የግድያ ወንጀል የፍርድ ውሳኔ አግኝቷል።
ሟች ህፃን ናኦድ ተኽላይ ሀምሌ 25 ቀን 2017 ዓ.ም በትግራይ ሰሜናዊ ምዕራብ ዞን እንዳስላሰ-ሽረ ከተማ ዙሪያ ነበር አሰቃቂ ግድያ የተፈፀመበት።
ግድያው የተፈጸመው ታግቶ ለማስለቀቂያ 2 ሚሊዮን ብር ከተጠየቀበት በኋላ ነው።
የሟች እናት ወ/ሮ ዮርዳኖስ ጋይም " በልጄ ግድያ ቁጥር አንድ ተጠርጣሪ የሆነው የቅርብ ቤተሰብ በህግ ቁጥጥር ስር ቢሆንም እስከ አሁን የተሰጠው የፍርድ ውሳኔ የለም " በማለት የፍትህ መዘግየቱ እጅግ እንዳሳዘናቸው መግለፃቸውን አስነብበን ነበር።
" የዘገየ ፍትህ እንዳልተሰጠ ይቆጠራል " ሲሉ ነበር የሟች እናት የገለጹት።
ጭካኔ የተሞላበት የግድያ አፈፃፀሙ ከአንድ ዓመት በላይ ሲከታተል የቆየው የሰሜናዊ ምዕራብ ዞን ማእከላዊ ፍርድ ቤት ዛሬ ማክሰኞ መጋቢት 22/2018 ዓ.ም ባዋለው ችሎት በሦስት ወንጀለኞች ላይ የመጨረሻ ውሳኔ አስተላልፏል።
በዚሁ መሰረት ፦
- የሟች ህፃን ናኦድ እናት #ወንድም በሆነው አንደኛ ተከሳሽ ክብሮም ገ/ማርያም የሞት ቅጣት፤
- ከሰተ ደበብና ፀጋይ የተባሉ ተከሳሾች እያንዳንዳቸው የ23 ዓመት ፅኑ እስራት፤
- ወንጀሉን ፈፅሞ የተሰወረው አራተኛ ተከሳሽ ዓንዶም ገ/ሊባኖስ በሌለበት የ25 ዓመታት ፅኑ እስራት እንዲቀጡ ፍርድ ቤት መወሰኑ ተዘግቧል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #rip #deathpenalty #court #tigray #mekelle
#ethiopia | ላልተገባ ጥቅም ሲባል ህፃን ናኦድ ተኽላይን በአስቃቂ ጭካኔ የገደሉ አራት ወንጀለኞች ከሞት እስከ 23 ዓመት በሚደርስ ፅኑ እስራት ተቀጡ።
ከአራቱ ወንጀለኞች አንዱ በሌለበት የ25 ዓመት ፅኑ እስራት ተፈርዶበታል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ላለፉት ዘጠኝ ወራት ሲከታተለው የቆየው አሰቃቂ የግድያ ወንጀል የፍርድ ውሳኔ አግኝቷል።
ሟች ህፃን ናኦድ ተኽላይ ሀምሌ 25 ቀን 2017 ዓ.ም በትግራይ ሰሜናዊ ምዕራብ ዞን እንዳስላሰ-ሽረ ከተማ ዙሪያ ነበር አሰቃቂ ግድያ የተፈፀመበት።
ግድያው የተፈጸመው ታግቶ ለማስለቀቂያ 2 ሚሊዮን ብር ከተጠየቀበት በኋላ ነው።
የሟች እናት ወ/ሮ ዮርዳኖስ ጋይም " በልጄ ግድያ ቁጥር አንድ ተጠርጣሪ የሆነው የቅርብ ቤተሰብ በህግ ቁጥጥር ስር ቢሆንም እስከ አሁን የተሰጠው የፍርድ ውሳኔ የለም " በማለት የፍትህ መዘግየቱ እጅግ እንዳሳዘናቸው መግለፃቸውን አስነብበን ነበር።
" የዘገየ ፍትህ እንዳልተሰጠ ይቆጠራል " ሲሉ ነበር የሟች እናት የገለጹት።
ጭካኔ የተሞላበት የግድያ አፈፃፀሙ ከአንድ ዓመት በላይ ሲከታተል የቆየው የሰሜናዊ ምዕራብ ዞን ማእከላዊ ፍርድ ቤት ዛሬ ማክሰኞ መጋቢት 22/2018 ዓ.ም ባዋለው ችሎት በሦስት ወንጀለኞች ላይ የመጨረሻ ውሳኔ አስተላልፏል።
በዚሁ መሰረት ፦
- የሟች ህፃን ናኦድ እናት #ወንድም በሆነው አንደኛ ተከሳሽ ክብሮም ገ/ማርያም የሞት ቅጣት፤
- ከሰተ ደበብና ፀጋይ የተባሉ ተከሳሾች እያንዳንዳቸው የ23 ዓመት ፅኑ እስራት፤
- ወንጀሉን ፈፅሞ የተሰወረው አራተኛ ተከሳሽ ዓንዶም ገ/ሊባኖስ በሌለበት የ25 ዓመታት ፅኑ እስራት እንዲቀጡ ፍርድ ቤት መወሰኑ ተዘግቧል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #rip #deathpenalty #court #tigray #mekelle
5 months ago
ሳዑዲ ዓረቢያ በ2025 በታሪኳ ከፍተኛውን የሞት ቅጣት መፈጸሟ ተገለጸ፤ 356 ሰዎችን ቀጥታለች
#ethiopia | ሳዑዲ ዓረቢያ በተጠናቀቀው የ2025 የፈረንጆቹ ዓመት 356 ሰዎችን በሞት መቅጣቷ ተነገረ። ይህም ሀገሪቱ በአንድ ዓመት ውስጥ የፈጸመችው ከፍተኛው የሞት ቅጣት ቁጥር ሆኖ መመዝገቡ ተገልጿል።
ከእፅ ዝውውር ጋር የተያያዘው የቅጣት ጭማሪ
ለተመዘገበው ከፍተኛ ቁጥር ዋነኛው ምክንያት ከእፅ ዝውውር ጋር የተያያዙ ወንጀሎች መሆናቸው ታውቋል። ከጠቅላላው የሞት ቅጣት ሰለባዎች መካከል 243ቱ (ወይም 68 በመቶ ያህሉ) ከእፅ ዝውውር ጋር በተያያዘ የተከሰሱ መሆናቸው ተመልክቷል።
የፖሊሲ ለውጥ🔎
ሳዑዲ ዓረቢያ በ2022 እ.ኤ.አ ከእፅ ጋር በተያያዙ ወንጀሎች ሰዎችን በሞት መቅጣት አቁማ የነበረ ቢሆንም፣ በ2025 ግን ይህንን አሠራር ዳግም አስጀምራለች። ይህ የቅጣት እርምጃ በአንድ ዓመት ውስጥ በዚህ መጠን ሲፈጸም በሀገሪቱ ታሪክ የመጀመሪያው መሆኑን መረጃዎች ያመለክታሉ።
ዓለም አቀፍ ስጋት 🎲
ይህ በከፍተኛ ሁኔታ የጨመረው የሞት ቅጣት አፈጻጸም በዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች ዘንድ ከፍተኛ ስጋትን ፈጥሯል። በተለይም ሀገሪቱ ቀደም ሲል የጀመረችውን የማሻሻያ እርምጃዎች ወደኋላ የሚመልስ ነው በሚል ትችቶች እየቀረቡባት ይገኛሉ።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#ሳዑዲዓረቢያ #የሞትቅጣት #እፅዝውውር #ሰብዓዊመብት #ዓለምአቀፍዜና #ሪያድ #saudiarabia #deathpenalty #drugtrafficking #humanrights #news
#ethiopia | ሳዑዲ ዓረቢያ በተጠናቀቀው የ2025 የፈረንጆቹ ዓመት 356 ሰዎችን በሞት መቅጣቷ ተነገረ። ይህም ሀገሪቱ በአንድ ዓመት ውስጥ የፈጸመችው ከፍተኛው የሞት ቅጣት ቁጥር ሆኖ መመዝገቡ ተገልጿል።
ከእፅ ዝውውር ጋር የተያያዘው የቅጣት ጭማሪ
ለተመዘገበው ከፍተኛ ቁጥር ዋነኛው ምክንያት ከእፅ ዝውውር ጋር የተያያዙ ወንጀሎች መሆናቸው ታውቋል። ከጠቅላላው የሞት ቅጣት ሰለባዎች መካከል 243ቱ (ወይም 68 በመቶ ያህሉ) ከእፅ ዝውውር ጋር በተያያዘ የተከሰሱ መሆናቸው ተመልክቷል።
የፖሊሲ ለውጥ🔎
ሳዑዲ ዓረቢያ በ2022 እ.ኤ.አ ከእፅ ጋር በተያያዙ ወንጀሎች ሰዎችን በሞት መቅጣት አቁማ የነበረ ቢሆንም፣ በ2025 ግን ይህንን አሠራር ዳግም አስጀምራለች። ይህ የቅጣት እርምጃ በአንድ ዓመት ውስጥ በዚህ መጠን ሲፈጸም በሀገሪቱ ታሪክ የመጀመሪያው መሆኑን መረጃዎች ያመለክታሉ።
ዓለም አቀፍ ስጋት 🎲
ይህ በከፍተኛ ሁኔታ የጨመረው የሞት ቅጣት አፈጻጸም በዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች ዘንድ ከፍተኛ ስጋትን ፈጥሯል። በተለይም ሀገሪቱ ቀደም ሲል የጀመረችውን የማሻሻያ እርምጃዎች ወደኋላ የሚመልስ ነው በሚል ትችቶች እየቀረቡባት ይገኛሉ።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#ሳዑዲዓረቢያ #የሞትቅጣት #እፅዝውውር #ሰብዓዊመብት #ዓለምአቀፍዜና #ሪያድ #saudiarabia #deathpenalty #drugtrafficking #humanrights #news