7 months ago
300,000 (ሶስት መቶ ሺህ) ብር በስህተት ወደ አካውንታችሁ ቢገባ ምን ታደርጋላችሁ?
* "የሰው ሀቅ ለኔ አይገባም!" - ወጣት እመቤት መኮንን
#ethiopia | ዛሬ ማለዳ በአዲስ አበባ አያት አካባቢ ነዋሪ የሆነችው ወጣት እመቤት መኮንን (በጓደኞቿ እሙ)፤ ያልጠበቀችው መልዕክት ስልኳ ላይ ገባ። መልዕክቱ 300,000 (ሶስት መቶ ሺህ) ብር ወደ ሂሳቧ መግባቱን የሚያበስር ነበር።
ገንዘቡ የሷ እንዳልሆነ ያወቀችው እመቤት፤ ለአፍታም ሳታመነታ "ይህ የሰው ሀቅ ነው፤ የኔ አይደለም" በማለት ለራሷ ወሰነች።
ከደቂቃዎች በኋላ ገንዘቡን በስህተት የላከውና በአላማጣ ከተማ የሚኖረው ወጣት መሐመድ መኪ ደውሎ ሲያናግራት፤ በፍጥነት እና በቅንነት ገንዘቡን ለመመለስ ተባበረችው።
የወጣት እመቤት መልእክት፡-
"እኔም በላቤ የምኖር ሰው ነኝ። ሰው በላቡ ለፍቶ ያገኘውን ገንዘብ በስህተት ወደ ሌላ ሰው መላክ ሊያጋጥም ይችላል፤ የራስ ያልሆነን ነገር መመለስ ግን ለኅሊና ዕረፍት ነው።"
የባለቤቱ ምስጋና፡-
ከአላማጣ ሆኖ በጭንቀት ይደውል የነበረው መሐመድ፤ በወጣቷ ምላሽ ተደናቋል። "ደውለን ስናናግራት የሰጠችን ምላሽ እምነቷንና ታማኝነቷን እንድገነዘብ አድርጎኛል። አላህ ሀቋን ይክፈላት" ሲል መርቋታል።
ክብር ለእንደዚህ አይነት ቅን ኢትዮጵያውያን! 👏
እናንተስ በወጣት እመቤት ቦታ ብትሆኑ ምን ታደርጉ ነበር? ሀሳባችሁን አጋሩን! 👇
#honesty #integrity #ethiopia #addisababa #alamata #gooddeed #inspiration
* "የሰው ሀቅ ለኔ አይገባም!" - ወጣት እመቤት መኮንን
#ethiopia | ዛሬ ማለዳ በአዲስ አበባ አያት አካባቢ ነዋሪ የሆነችው ወጣት እመቤት መኮንን (በጓደኞቿ እሙ)፤ ያልጠበቀችው መልዕክት ስልኳ ላይ ገባ። መልዕክቱ 300,000 (ሶስት መቶ ሺህ) ብር ወደ ሂሳቧ መግባቱን የሚያበስር ነበር።
ገንዘቡ የሷ እንዳልሆነ ያወቀችው እመቤት፤ ለአፍታም ሳታመነታ "ይህ የሰው ሀቅ ነው፤ የኔ አይደለም" በማለት ለራሷ ወሰነች።
ከደቂቃዎች በኋላ ገንዘቡን በስህተት የላከውና በአላማጣ ከተማ የሚኖረው ወጣት መሐመድ መኪ ደውሎ ሲያናግራት፤ በፍጥነት እና በቅንነት ገንዘቡን ለመመለስ ተባበረችው።
የወጣት እመቤት መልእክት፡-
"እኔም በላቤ የምኖር ሰው ነኝ። ሰው በላቡ ለፍቶ ያገኘውን ገንዘብ በስህተት ወደ ሌላ ሰው መላክ ሊያጋጥም ይችላል፤ የራስ ያልሆነን ነገር መመለስ ግን ለኅሊና ዕረፍት ነው።"
የባለቤቱ ምስጋና፡-
ከአላማጣ ሆኖ በጭንቀት ይደውል የነበረው መሐመድ፤ በወጣቷ ምላሽ ተደናቋል። "ደውለን ስናናግራት የሰጠችን ምላሽ እምነቷንና ታማኝነቷን እንድገነዘብ አድርጎኛል። አላህ ሀቋን ይክፈላት" ሲል መርቋታል።
ክብር ለእንደዚህ አይነት ቅን ኢትዮጵያውያን! 👏
እናንተስ በወጣት እመቤት ቦታ ብትሆኑ ምን ታደርጉ ነበር? ሀሳባችሁን አጋሩን! 👇
#honesty #integrity #ethiopia #addisababa #alamata #gooddeed #inspiration
8 months ago
ራስን በራስ ማስተዳደር እስከ መገንጠል
የሕገመንግስት አንቀጽ 39 እና ዓለም አቀፍ ህጎች
በህግ ባለሙያ ፋንታሁን ደለለው
መግቢያ #ethiopia | በአለምአቀፍ ደረጃ ራስን በራስ ማስተዳደር /self determination/ ጽነስ ሀሳቡ እስከ የት ድረስ እንደሆነ የተለያየ ትርጉም ሲሰጥበት ይስተዋላል። አንዳንዶች የመገንጠልን ጽንሰ ሀሳብን የሚያካትቱ ሲሆን አንዳንዳቹ ደግሞ የመገንጠልን ጽንሰሀሳብ በፍጹም በህገመንግስታቸው ውስጥ ሳያካትቱ እንደውም መገንጠል ላይ በዝምታም ሆነ በግልጽ የሚከለክሉ ሀገራት አሉ።
ራስን በራስ እስከ ማስተዳደር መገንጠል ስረአት በህገመንግስታቸው የሚያካትቱ ሀገራት ደግሞ በግልጽ እንዴት ሊሆን እንደሚችል በግልጽ አስቀምጠዋል። ከዚህ ውጭ ባለፈም በህጋዊ ህጋዊ ባልሆነ መንገድ ተገንጥለው ሀገር ነን የሚሉ እያስተዋልናቸው ያለ ሲሆን እነዚህ ሀገራት "እጣፋንታቸው ምንድነው?" የሚለውን በዚህ አጭር ጽሁፍ የምንመለከተው ይሆናል
1. ራስን በራስ ማስተዳደር ምንድነው?
(self determination)
ራስን በራስ ማስተዳደር አንድ ሀገር ወይም የአንድ ሀገር ክልል የሀገሩን የህገመንግስት እና የህግ የበላይነት በማክበር ያለማንም ጣልቃ ገብነት ራሳቸውን በራሳቸው እድል የሚያስተዳድረበት ነው። በዚህ ረገድ የተለያየ አይነት ዙርያ ጥምጥም አይነት ትርጉም ቢመላለስም ራስን በራስ ማስተዳደር ማለት ከማንም ከጣልቃገብነት ነጻ በመሆን በህግ የበላይነትና በህዝቦች መፈቃቀድ ላይ የተመሰረተ አስተዳደር ነው።
2. ራስን በራስ ማስተዳደር እስከመገንጠል እንዴት ይፈጸማል? self determination to succesion
ራስን በራስ ማስዳደር እስከ መገንጠልን ተግባራዊ ለማድረግ የሚፈልግ ሀገር ከነበረበት ሀገር ጋር ለመቀጠል የሚያስችለው ዲሞክሪያሳዊ ፣ ህገመንግስታዊ መብትን ፣ አለምአቀፍ የዲሞክሪያሳዊ እና የሰብአዊ መብቶችን ለመጎናጻፍ ከእናት ሀገሩ ያጣ እንደሆና በህዝቡ ላይ ተደጋጋሚ የመብት ጭቆና እና የመብት ጥሰት እየደረሰበት ከሆነ ነው።
በዚህ ጊዜ ራስን በራስ የማስተዳደር እስከ መገንጠል መብት ጥያቄው ለሀገረ መንግስቱ ለሀገረ መንግስቱ መብት የተሰጠው ሲሆን ይህን በማቅረብ ህጉን ተከትሎ የሚወሰን ይሆናል።
ከዚያም በሀገሩ ህዝብና ህገመንግስት መሠረት በማድረግ አጠቃላይ ውሳኔ መገንጠል የሚፈልገው ህዝብ ጭምር ተጠይቆ የመጨረሻ መልሱ ያለ ልዩነት የመገንጠል መብትን የሚፈቅድ ከሆነ መገንጠል ተግባራዊ ይሆናል።
ይህ የሚሆነውም የመገንጠል መብት በህጉ በግልጽ የተቀመጠ እንደሆነ ነው። አለበለዚያ ግን መገንጠል አይታሰብም ተገነጠልኩ ቢልም የቅዥት ተግባር ይሆናል እንጂ ህጉን የጠበቀ ተግባር አይሆንም።
3. ራስን በራስ ማስተዳደር እስከ መገንጠል ተግባር እንዴት ይፈጸማል?
በመጀመሪያ ደረጃ የመጀመሪያዋ ሀገር የመገንጠል ጥያቄ የሚቀርብባት ህጋዊ ሀገር ልትሆን ያስፈልጋል። ይህም ማለት በአለም አቀፍ ልምድ ህጎች ውሳኔዎች መሠረት ሀገር ለማለት የምትበቃ ልትሆን ያስፈልጋል።
ሀገር ስትሆን የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፣ህግ አውጪ፣ ህግ አስፈጻሚ ፣ህገመንግስት፣ህዝብ፣ግዛት፣የውጭ ግንኙነት አቅም ፣ ሉአላዊነት ሊኖራት ያስፈልጋል።
ይህቺ ሀገር በዚህ ልክ ህጋዊ ከሆነች በኋላ ነው የመገንጠል ጥያቄን የተወሰነው ሀገረ ግዛት ወይም ክልል ራስን በራስ ማስተዳደር ወይም እስከ መገንጠል የሚለውን በመጠየቅ በጠያቂው ህዝብ፣ ግዛትና እና በተጠያቂው ሀገር ህዝብ ሙሉ ፍቃድ ተፈጻሚ የሚሆነው።
ለምሳሌ ከኢትዮጵያ መገንጠል የሚፈልግ ክልል የሁሉም ክልሎች ፣ የፌደራል ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤ፥ የፌድሬሽን ምክር ቤት እንዲሁም የጠያቂው ክልል ምክር ቤት በሙሉ ያለ ምንም ልዩነት የመገንጠል ይሁንታን ሊገኝ ያስፈልጋል።
አንዱ እንኳን የልዩነት ሀሳብ ካመጣ የመገንጠል ሀሳብ ተግባራዊ ሊሆን አይችልም። ይህ በኢፊድሪ ከመንግሥት አንቀጽ 39 ላይ የተቀመጠ ነው።
ለምሳሌ በኢትዮጵያ ይህ ህገመንግስት ሳይወጣ መንግስት ሳይመረጥ የመገንጠል ስረአት የሚከናወንበት ህግና ህገመንግስት ሳይኖር ሀገርንና ህዝብን ወክሎ የውጭ ግንኙነቶች ጋር የድርድርና የማስፈጸም አቅም ያለው የፖለቲካ ፓርቲ ወደ መንግስት የተቀየረ ሳይኖር ሀገርን በበላይነት የሚገዛ ህመንግስት ሳይመሰረት በተረባበሸ የሀገር ስሜት ውስጥ በመሆን ተገንጥያለው ብሎ በተወሰኑ ቡድኖች ብቻ በተደረገ የማይጸና ውል የመገንጠል ጥያቄ አቅራቢውም ሆነ ተቀባይውም ህጋዊ ቅቡልነት የሌላቸው ናቸው።
3. ቅቡልነት ያለው ህግን ሳይከተሉ መገንጠልን በራሳቸው ህጋዊ ያደረጉ ሀገራት እጣ ፈንታቸው ምን ይሆናል?
እነዚህ ሀገራት by defacfo(ያለ ህግ ቅቡልነት) ያላቸው ቢሆንም ከሌሎች ሀገሮች ጋር በሚያደርጉት ግንኙነቶች የሌላን ሀገርን ብሔራዊ ጥቅም መብት የሚነካ ከሆነ ጥቅሙ የሚነካበት ሀገር በተለይም ሀገር የሆነበት አካሄድ ህጋዊ ጥያቄን የሚያስነሳ ከሆነ ይህንን በመቃወሚያነት በማንሳት ብሔራዊ ጥቅሙ የተነካበት ሀገር መብቱን ማስከበር ይችላል።
4. መደምደሚያ
ይህ እንደ ጸሀፊው የህግ ምርምርና አስተያየት የቀረበ ቢሆንም ዋናው ነገር እንደ ጸሀፊው አስተያየት ሀገራት እንደ ህጋዊ ሀገር ሆነው ህዝባቸውን በማስተዳደር የዜጎችን እና የሀገርን ሉአላዊነት ለማስጠበቅ በመጀመረያ ደረጃ በህግ ቅቡልነት ሊኖራቸው ያስፈልጋል።
References/ዋቢ መጽሀፍት/
1. Crawford, J. (2006). The Creation of States in International Law (2nd ed.). Oxford University Press.
2. International Court of Justice (ICJ). (2010). Accordance with International Law of the Unilateral Declaration of Independence in Respect of Kosovo, Advisory Opinion.
3. International Court of Justice (ICJ). (1986). Frontier Dispute (Burkina Faso/Republic of Mali), Judgment.
4. Montevideo Convention on the Rights and Duties of States. (1933).
5. United Nations Human Rights Council (UNHRC). (2022). Report of the Special Rapporteur on the situation of human rights in Eritrea. A/HRC/50/20.
6. United Nations Security Council (UNSC). (1999). Resolution 1244. S/RES/1244.
7. United Nations Security Council (UNSC). (1961). Resolution 169. S/RES/169.
8. Vaughan, S. (2011). The Ethio-Eritrean Conflict and the Algiers Agreement: A Legal Analysis. In A. Jacquin-Berdal & M. Plaut (Eds.), Unfinished Business: Ethiopia and Eritrea at War. Red Sea Press.
9. Woods, T. (2019). The Law of Territorial Integrity and the Eritrea-Ethiopia Boundary Commission. Cambridge Journal of International and Comparative Law.
የሕገመንግስት አንቀጽ 39 እና ዓለም አቀፍ ህጎች
በህግ ባለሙያ ፋንታሁን ደለለው
መግቢያ #ethiopia | በአለምአቀፍ ደረጃ ራስን በራስ ማስተዳደር /self determination/ ጽነስ ሀሳቡ እስከ የት ድረስ እንደሆነ የተለያየ ትርጉም ሲሰጥበት ይስተዋላል። አንዳንዶች የመገንጠልን ጽንሰ ሀሳብን የሚያካትቱ ሲሆን አንዳንዳቹ ደግሞ የመገንጠልን ጽንሰሀሳብ በፍጹም በህገመንግስታቸው ውስጥ ሳያካትቱ እንደውም መገንጠል ላይ በዝምታም ሆነ በግልጽ የሚከለክሉ ሀገራት አሉ።
ራስን በራስ እስከ ማስተዳደር መገንጠል ስረአት በህገመንግስታቸው የሚያካትቱ ሀገራት ደግሞ በግልጽ እንዴት ሊሆን እንደሚችል በግልጽ አስቀምጠዋል። ከዚህ ውጭ ባለፈም በህጋዊ ህጋዊ ባልሆነ መንገድ ተገንጥለው ሀገር ነን የሚሉ እያስተዋልናቸው ያለ ሲሆን እነዚህ ሀገራት "እጣፋንታቸው ምንድነው?" የሚለውን በዚህ አጭር ጽሁፍ የምንመለከተው ይሆናል
1. ራስን በራስ ማስተዳደር ምንድነው?
(self determination)
ራስን በራስ ማስተዳደር አንድ ሀገር ወይም የአንድ ሀገር ክልል የሀገሩን የህገመንግስት እና የህግ የበላይነት በማክበር ያለማንም ጣልቃ ገብነት ራሳቸውን በራሳቸው እድል የሚያስተዳድረበት ነው። በዚህ ረገድ የተለያየ አይነት ዙርያ ጥምጥም አይነት ትርጉም ቢመላለስም ራስን በራስ ማስተዳደር ማለት ከማንም ከጣልቃገብነት ነጻ በመሆን በህግ የበላይነትና በህዝቦች መፈቃቀድ ላይ የተመሰረተ አስተዳደር ነው።
2. ራስን በራስ ማስተዳደር እስከመገንጠል እንዴት ይፈጸማል? self determination to succesion
ራስን በራስ ማስዳደር እስከ መገንጠልን ተግባራዊ ለማድረግ የሚፈልግ ሀገር ከነበረበት ሀገር ጋር ለመቀጠል የሚያስችለው ዲሞክሪያሳዊ ፣ ህገመንግስታዊ መብትን ፣ አለምአቀፍ የዲሞክሪያሳዊ እና የሰብአዊ መብቶችን ለመጎናጻፍ ከእናት ሀገሩ ያጣ እንደሆና በህዝቡ ላይ ተደጋጋሚ የመብት ጭቆና እና የመብት ጥሰት እየደረሰበት ከሆነ ነው።
በዚህ ጊዜ ራስን በራስ የማስተዳደር እስከ መገንጠል መብት ጥያቄው ለሀገረ መንግስቱ ለሀገረ መንግስቱ መብት የተሰጠው ሲሆን ይህን በማቅረብ ህጉን ተከትሎ የሚወሰን ይሆናል።
ከዚያም በሀገሩ ህዝብና ህገመንግስት መሠረት በማድረግ አጠቃላይ ውሳኔ መገንጠል የሚፈልገው ህዝብ ጭምር ተጠይቆ የመጨረሻ መልሱ ያለ ልዩነት የመገንጠል መብትን የሚፈቅድ ከሆነ መገንጠል ተግባራዊ ይሆናል።
ይህ የሚሆነውም የመገንጠል መብት በህጉ በግልጽ የተቀመጠ እንደሆነ ነው። አለበለዚያ ግን መገንጠል አይታሰብም ተገነጠልኩ ቢልም የቅዥት ተግባር ይሆናል እንጂ ህጉን የጠበቀ ተግባር አይሆንም።
3. ራስን በራስ ማስተዳደር እስከ መገንጠል ተግባር እንዴት ይፈጸማል?
በመጀመሪያ ደረጃ የመጀመሪያዋ ሀገር የመገንጠል ጥያቄ የሚቀርብባት ህጋዊ ሀገር ልትሆን ያስፈልጋል። ይህም ማለት በአለም አቀፍ ልምድ ህጎች ውሳኔዎች መሠረት ሀገር ለማለት የምትበቃ ልትሆን ያስፈልጋል።
ሀገር ስትሆን የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፣ህግ አውጪ፣ ህግ አስፈጻሚ ፣ህገመንግስት፣ህዝብ፣ግዛት፣የውጭ ግንኙነት አቅም ፣ ሉአላዊነት ሊኖራት ያስፈልጋል።
ይህቺ ሀገር በዚህ ልክ ህጋዊ ከሆነች በኋላ ነው የመገንጠል ጥያቄን የተወሰነው ሀገረ ግዛት ወይም ክልል ራስን በራስ ማስተዳደር ወይም እስከ መገንጠል የሚለውን በመጠየቅ በጠያቂው ህዝብ፣ ግዛትና እና በተጠያቂው ሀገር ህዝብ ሙሉ ፍቃድ ተፈጻሚ የሚሆነው።
ለምሳሌ ከኢትዮጵያ መገንጠል የሚፈልግ ክልል የሁሉም ክልሎች ፣ የፌደራል ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤ፥ የፌድሬሽን ምክር ቤት እንዲሁም የጠያቂው ክልል ምክር ቤት በሙሉ ያለ ምንም ልዩነት የመገንጠል ይሁንታን ሊገኝ ያስፈልጋል።
አንዱ እንኳን የልዩነት ሀሳብ ካመጣ የመገንጠል ሀሳብ ተግባራዊ ሊሆን አይችልም። ይህ በኢፊድሪ ከመንግሥት አንቀጽ 39 ላይ የተቀመጠ ነው።
ለምሳሌ በኢትዮጵያ ይህ ህገመንግስት ሳይወጣ መንግስት ሳይመረጥ የመገንጠል ስረአት የሚከናወንበት ህግና ህገመንግስት ሳይኖር ሀገርንና ህዝብን ወክሎ የውጭ ግንኙነቶች ጋር የድርድርና የማስፈጸም አቅም ያለው የፖለቲካ ፓርቲ ወደ መንግስት የተቀየረ ሳይኖር ሀገርን በበላይነት የሚገዛ ህመንግስት ሳይመሰረት በተረባበሸ የሀገር ስሜት ውስጥ በመሆን ተገንጥያለው ብሎ በተወሰኑ ቡድኖች ብቻ በተደረገ የማይጸና ውል የመገንጠል ጥያቄ አቅራቢውም ሆነ ተቀባይውም ህጋዊ ቅቡልነት የሌላቸው ናቸው።
3. ቅቡልነት ያለው ህግን ሳይከተሉ መገንጠልን በራሳቸው ህጋዊ ያደረጉ ሀገራት እጣ ፈንታቸው ምን ይሆናል?
እነዚህ ሀገራት by defacfo(ያለ ህግ ቅቡልነት) ያላቸው ቢሆንም ከሌሎች ሀገሮች ጋር በሚያደርጉት ግንኙነቶች የሌላን ሀገርን ብሔራዊ ጥቅም መብት የሚነካ ከሆነ ጥቅሙ የሚነካበት ሀገር በተለይም ሀገር የሆነበት አካሄድ ህጋዊ ጥያቄን የሚያስነሳ ከሆነ ይህንን በመቃወሚያነት በማንሳት ብሔራዊ ጥቅሙ የተነካበት ሀገር መብቱን ማስከበር ይችላል።
4. መደምደሚያ
ይህ እንደ ጸሀፊው የህግ ምርምርና አስተያየት የቀረበ ቢሆንም ዋናው ነገር እንደ ጸሀፊው አስተያየት ሀገራት እንደ ህጋዊ ሀገር ሆነው ህዝባቸውን በማስተዳደር የዜጎችን እና የሀገርን ሉአላዊነት ለማስጠበቅ በመጀመረያ ደረጃ በህግ ቅቡልነት ሊኖራቸው ያስፈልጋል።
References/ዋቢ መጽሀፍት/
1. Crawford, J. (2006). The Creation of States in International Law (2nd ed.). Oxford University Press.
2. International Court of Justice (ICJ). (2010). Accordance with International Law of the Unilateral Declaration of Independence in Respect of Kosovo, Advisory Opinion.
3. International Court of Justice (ICJ). (1986). Frontier Dispute (Burkina Faso/Republic of Mali), Judgment.
4. Montevideo Convention on the Rights and Duties of States. (1933).
5. United Nations Human Rights Council (UNHRC). (2022). Report of the Special Rapporteur on the situation of human rights in Eritrea. A/HRC/50/20.
6. United Nations Security Council (UNSC). (1999). Resolution 1244. S/RES/1244.
7. United Nations Security Council (UNSC). (1961). Resolution 169. S/RES/169.
8. Vaughan, S. (2011). The Ethio-Eritrean Conflict and the Algiers Agreement: A Legal Analysis. In A. Jacquin-Berdal & M. Plaut (Eds.), Unfinished Business: Ethiopia and Eritrea at War. Red Sea Press.
9. Woods, T. (2019). The Law of Territorial Integrity and the Eritrea-Ethiopia Boundary Commission. Cambridge Journal of International and Comparative Law.
9 months ago
ግለሰብ እና ብሔራዊ ጥቅም...
(የሀብታሙ ደባሱ አዲሱ የግል ሀሳብ)
#ethiopia | እውቁ የፖለቲካ ሳይንቲስት እና የአለምአቀፍ ግንኙነት ሊቃውንት ጆሴፍ ፍራንከል "International Relations in a Changing World " በሚለው መጽሐፉ እና በአጠቃላይ፣ይህ ርዕስ በዓለም አቀፍ ግንኙነት ጥናት (International Relations) ትምህርት መስክ በሁሉም ህልዬቶች ከመጀመሪያው የንድፈ-ሀሳብ ትንተና "የብሔራዊ ጥቅምን (National Interest ) ጉዳይ በሚገባ ያስረዳል።
ብሔራዊ ጥቅም በአንድ ሉዓላዊ ሀገር መንግስት ዘላቂነት ባለው መልኩ ሊያሳካቸው የሚፈልጋቸው ዋና ዋና ግቦች፣ዓላማዎች እና ፍላጎቶች ድምር ውጤት ነው።እነዚህ ፍላጎቶች የሀገሪቱን ህልውና፣ደህንነት ፣ልማትና እና ብልጽግን ለማረጋገጥ ወሳኝ ናቸው።
ብሔራዊ ጥቅምን የሚወስኑት መሠረታዊ ነገሮች ደህንነት እና ሕልውና (Survival and Security) የግዛት ሉዓላዊነት እና አንድነት (Sovereignty and Territorial Integrity) የሀገሪቱን ድንበሮች ማስጠበቅ እና የውስጥ አስተዳደር በውጭ ጣልቃ ገብነት አለመወሰኑን ማረጋገጥ በጥብቅ መከታተል እና የፀጥታ እና የደህንነት ተቋማትን የመከላከያ፣ደህነት ዘርፍን ማዘመን እና ዘመናዊነቱን ማጠናከርንም ይጨምራል።ይህ ሂደት የዜጎች ሰላም አስተማማኝነት የሀገሪቱን ዜጎች ከውስጥም ሆነ ከውጭ አደጋዎች መጠበቅ ያጠቃልላል ።
ብልጽግና እና ደኅንነት (Prosperity and Welfare) ኢኮኖሚያዊ ልማት፤የዜጎችን ኑሮ ማሻሻል፣ድህነትን መቀነስ፣ዘላቂና ሁሉን ያካተተ ዕድገት በተለያዩ ዘርፎች ማስመዝገብ እና በበቂ ሁኔታ የውጭ እና አለምአቀፍ ንግድ (Foreign Trade)ፍላጎቶችን ሚዛናዊነት በመጠበቅ ለሀገር ብሔራዊ ልማት ግቦች የሚረዱ የኢኮኖሚ ምንጮችንና መውጫዎችን ማረጋገጥ (እንደ ወደብና የትራንስፖርት መስመሮች፣የየብስ እና የአየር ትራንስፖርትን ይጨምራል)።
በተጨማሪም ክብርና እሴቶች (Prestige and Values) በዓለም አቀፍ ደረጃ የሀገርን ክብርና ሞራል ከፍ ማድረግ ሲሆን በሕገ-መንግስቱ የተደነገጉ እሴቶችንና መርሆችን ማስጠበቅ (እንደ ሕብረ-ብሔራዊ አንድነት፣ዲሞክራሲ፣መልካም አስተዳደር ብልጽግና መሰል የታሪክ፣የዲፕሎማሲ ግንኙነት ከትውልድ ወደ ትውልድ ማፅናት)ይሆናል።
እንደ መውጫ :-
በየትኛውም የአለም ክፍል የሚገኝ የሀገር እና ህዝብ የብሔራዊ ጥቅምን ጉዳይ በጋራና ትብብር በአንድነት ይሰራል።ይህ ማለት"የፖለቲካ ሀሳብ ልዩነት" (Political Differences) በግለሰቦች፣በቡድኖች ወይም በአካባቢዎች መካከል ባሉ የፖለቲካ እምነቶች፣አስተሳሰቦች (Ideologies) እና ስርዓቶች ውስጥ የሚታዩ ልዩነቶች ቢኖሩም የአገር ብሔራዊ ጥቅም ጉዳይ ውስብስብ የሆነውን የፖለቲካ ልዩነት (Political Difference) እና የፖለቲካ አለመግባባት (Political Disagreement) ወደ ጎን በመተው ለዘላቂ ጥቅም ይሰራሉ።
ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም መሳካት የድርሻዬን እወጣለሁ !
#ethiopia 🇪🇹
(የሀብታሙ ደባሱ አዲሱ የግል ሀሳብ)
#ethiopia | እውቁ የፖለቲካ ሳይንቲስት እና የአለምአቀፍ ግንኙነት ሊቃውንት ጆሴፍ ፍራንከል "International Relations in a Changing World " በሚለው መጽሐፉ እና በአጠቃላይ፣ይህ ርዕስ በዓለም አቀፍ ግንኙነት ጥናት (International Relations) ትምህርት መስክ በሁሉም ህልዬቶች ከመጀመሪያው የንድፈ-ሀሳብ ትንተና "የብሔራዊ ጥቅምን (National Interest ) ጉዳይ በሚገባ ያስረዳል።
ብሔራዊ ጥቅም በአንድ ሉዓላዊ ሀገር መንግስት ዘላቂነት ባለው መልኩ ሊያሳካቸው የሚፈልጋቸው ዋና ዋና ግቦች፣ዓላማዎች እና ፍላጎቶች ድምር ውጤት ነው።እነዚህ ፍላጎቶች የሀገሪቱን ህልውና፣ደህንነት ፣ልማትና እና ብልጽግን ለማረጋገጥ ወሳኝ ናቸው።
ብሔራዊ ጥቅምን የሚወስኑት መሠረታዊ ነገሮች ደህንነት እና ሕልውና (Survival and Security) የግዛት ሉዓላዊነት እና አንድነት (Sovereignty and Territorial Integrity) የሀገሪቱን ድንበሮች ማስጠበቅ እና የውስጥ አስተዳደር በውጭ ጣልቃ ገብነት አለመወሰኑን ማረጋገጥ በጥብቅ መከታተል እና የፀጥታ እና የደህንነት ተቋማትን የመከላከያ፣ደህነት ዘርፍን ማዘመን እና ዘመናዊነቱን ማጠናከርንም ይጨምራል።ይህ ሂደት የዜጎች ሰላም አስተማማኝነት የሀገሪቱን ዜጎች ከውስጥም ሆነ ከውጭ አደጋዎች መጠበቅ ያጠቃልላል ።
ብልጽግና እና ደኅንነት (Prosperity and Welfare) ኢኮኖሚያዊ ልማት፤የዜጎችን ኑሮ ማሻሻል፣ድህነትን መቀነስ፣ዘላቂና ሁሉን ያካተተ ዕድገት በተለያዩ ዘርፎች ማስመዝገብ እና በበቂ ሁኔታ የውጭ እና አለምአቀፍ ንግድ (Foreign Trade)ፍላጎቶችን ሚዛናዊነት በመጠበቅ ለሀገር ብሔራዊ ልማት ግቦች የሚረዱ የኢኮኖሚ ምንጮችንና መውጫዎችን ማረጋገጥ (እንደ ወደብና የትራንስፖርት መስመሮች፣የየብስ እና የአየር ትራንስፖርትን ይጨምራል)።
በተጨማሪም ክብርና እሴቶች (Prestige and Values) በዓለም አቀፍ ደረጃ የሀገርን ክብርና ሞራል ከፍ ማድረግ ሲሆን በሕገ-መንግስቱ የተደነገጉ እሴቶችንና መርሆችን ማስጠበቅ (እንደ ሕብረ-ብሔራዊ አንድነት፣ዲሞክራሲ፣መልካም አስተዳደር ብልጽግና መሰል የታሪክ፣የዲፕሎማሲ ግንኙነት ከትውልድ ወደ ትውልድ ማፅናት)ይሆናል።
እንደ መውጫ :-
በየትኛውም የአለም ክፍል የሚገኝ የሀገር እና ህዝብ የብሔራዊ ጥቅምን ጉዳይ በጋራና ትብብር በአንድነት ይሰራል።ይህ ማለት"የፖለቲካ ሀሳብ ልዩነት" (Political Differences) በግለሰቦች፣በቡድኖች ወይም በአካባቢዎች መካከል ባሉ የፖለቲካ እምነቶች፣አስተሳሰቦች (Ideologies) እና ስርዓቶች ውስጥ የሚታዩ ልዩነቶች ቢኖሩም የአገር ብሔራዊ ጥቅም ጉዳይ ውስብስብ የሆነውን የፖለቲካ ልዩነት (Political Difference) እና የፖለቲካ አለመግባባት (Political Disagreement) ወደ ጎን በመተው ለዘላቂ ጥቅም ይሰራሉ።
ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም መሳካት የድርሻዬን እወጣለሁ !
#ethiopia 🇪🇹
10 months ago
የአትሌቷ ቅጣትና የሪከርዱ ጉዳይ እንዴት ይሆናል?
(ምስጋናው ታደሰ)
#ethiopia | Hydrochlorothiazide (ሀይድሮክሎራይዝድ) HCTZ የተባለ የተከለከለ አበረታች ንጥረ ነገር መጠቀሟ የተረጋገጠባት ኬንያዊቷ የሴቶች ማራቶን የዓለም ሪከርድ ባለቤት ሩት ቼፕንጌቲች የሶስት ዓመታት እገዳ እንደተጣለባት The Athletics Integrity Unit (AIU) ዛሬ (ሐሙስ) ባወጣው መግለጫ ማስታወቁን ገልጬ ፅፌያለሁ።
ይህንን ተከትሎም የሪከርዱ ጉዳይ እንዴት ይሆናል? ለቀድሞዋ የሪከርዱ ባለቤት ትዕግስት አሰፋ ይመለሳል ወይ? የሚሉ ጥያቄዎች እየተነሱ ይገኛሉ።
እናስ?
እናማ ሪከርዱ ወደ ትዕግስት አይመለስም፤ ከሩት ቼፕንጌቲች ጋር ይቆያል።
እንዴት ይህ ሊሆን ቻለ?
የ31 ዓመቷ ኬንያዊት "ሀይድሮክሎራይዝድ" የተባለውን የተከለከለ ንጥረ ነገር መውሰዷ የተረጋገጠባት ማርች 14/2025 በተደረገላት የደምና የሽንት ምርመራ ነው። በመሆኑም ከዛን ጊዜ አንስቶ ጊዜያዊ እገዳ ተጥሎባት የቆየ ሲሆን በዛሬው ዕለት ደግሞ የሶስት ዓመት እገዳ ተጥሎባታል።
የAIU ዋና ስራ አስፈፃሚ የሆኑት ብሬት ክሎዚዬ ጉዳዩን አስመልክተው በሰጡት አስተያየት እገዳው የሚፀናባት ምርመራው ከተደረገላት ከማርች 2025 ወዲህ መሆኑንና ከዛ በፊት የነበሩት ውጤቶቿ የዓለም ሪከርድን ጨምሮ በእጇ እንደሚቆዩ ማረጋገጫ ሰጥተዋል። ስለዚህ ሪከርዱ ወደ ትዕግስት አሰፋ አይመለስም።
ይሁንና ይሄ እስከ መጨረሻው የሚፀና ውሳኔ ላይሆን ይችላል። ምክንያቱም ይሄኛው ውጤት ይፋ ከሆነ በኋላ AIU ወደኋላ ተመልሶ በአትሌቷ ላይ ተጨማሪ ምርመራዎችን ጀምሯል።
ለምሳሌ በምርመራው ወቅት ቃለ-ምልልስ ሲደረግላት "ባመመኝ ሰዓት ይሄንን ሀይድሮክሎራይዝድ ጨምሮ ሌሎችንም የባህል መድሃኒቶችን የምትሰጠኝ የቤት ሰራተኛዬ ናት" የሚል ቃል ሰጥታለች። በዚህም ሰራተኛዋም ምርመራ እየተደረገባት ነው።
ቼፕንጌቲች "Rosa Associati" በተባለው የአትሌቲክስ ማኔጅመንት ስር ነው የምትወዳደረው። የዚህ ኩባንያ ባለቤት ጣልያናዊው ፌዴሪኮ ሮሳ (በ2ኛው ፎቶ የሚታየው) ነው።
ይህ ሰው ከ30 በላይ ስመጥር ኬንያውያን አትሌቶችን በስሩ የሚያስተዳድር ሲሆን ከዶፒንግ ጋር በተያያዘ ለቅጣት ከሚዳረጉት በርካታ የሀገሪቱ አትሌቶች መካከልም አብዛኛዎቹ በእሱ ስር የሚወዳደሩ ናቸው። የኬንያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ከኦገስት 2025 አንስቶ እገዳ ጥሎበታል። ይህንን ተከትሎም እሱም በAIU ምርመራ እየተደረገበት ነው።
ይህም ብቻ ሳይሆን የቼፕንጌቲች የሞባይል ስልክ ላይም ምርመራ እየተደረገ ነው። አትሌቷ መጀመሪያ ላይ ሞባይሏን ላለማስፈተሽ አንገራግራ የነበረ ቢሆንም በኋላ ላይ ግን ተስማምታለች። ከፌዴሪኮ ሮሳ ጋር የተፃፃፈቻቸው መልዕክቶች እና የመድሃኒት ፎቶዎች እየተመረመሩ ነው።
የእነዚህ ምርመራ ገና በሂደት ላይ ነው። ወደ ኋላ ተሂዶ እየተደረገ ባለው ምርመራና የመጨረሻ ውጤት ከዚህ በፊትም ዶፒንግ ትወስድ እንደነበር ከተረጋገጠባት ሪከርዱን ልትነጠቅና ለትዕግስት አሰፋ ሊመለስላት ይችላል።
(ምስጋናው ታደሰ)
#ethiopia | Hydrochlorothiazide (ሀይድሮክሎራይዝድ) HCTZ የተባለ የተከለከለ አበረታች ንጥረ ነገር መጠቀሟ የተረጋገጠባት ኬንያዊቷ የሴቶች ማራቶን የዓለም ሪከርድ ባለቤት ሩት ቼፕንጌቲች የሶስት ዓመታት እገዳ እንደተጣለባት The Athletics Integrity Unit (AIU) ዛሬ (ሐሙስ) ባወጣው መግለጫ ማስታወቁን ገልጬ ፅፌያለሁ።
ይህንን ተከትሎም የሪከርዱ ጉዳይ እንዴት ይሆናል? ለቀድሞዋ የሪከርዱ ባለቤት ትዕግስት አሰፋ ይመለሳል ወይ? የሚሉ ጥያቄዎች እየተነሱ ይገኛሉ።
እናስ?
እናማ ሪከርዱ ወደ ትዕግስት አይመለስም፤ ከሩት ቼፕንጌቲች ጋር ይቆያል።
እንዴት ይህ ሊሆን ቻለ?
የ31 ዓመቷ ኬንያዊት "ሀይድሮክሎራይዝድ" የተባለውን የተከለከለ ንጥረ ነገር መውሰዷ የተረጋገጠባት ማርች 14/2025 በተደረገላት የደምና የሽንት ምርመራ ነው። በመሆኑም ከዛን ጊዜ አንስቶ ጊዜያዊ እገዳ ተጥሎባት የቆየ ሲሆን በዛሬው ዕለት ደግሞ የሶስት ዓመት እገዳ ተጥሎባታል።
የAIU ዋና ስራ አስፈፃሚ የሆኑት ብሬት ክሎዚዬ ጉዳዩን አስመልክተው በሰጡት አስተያየት እገዳው የሚፀናባት ምርመራው ከተደረገላት ከማርች 2025 ወዲህ መሆኑንና ከዛ በፊት የነበሩት ውጤቶቿ የዓለም ሪከርድን ጨምሮ በእጇ እንደሚቆዩ ማረጋገጫ ሰጥተዋል። ስለዚህ ሪከርዱ ወደ ትዕግስት አሰፋ አይመለስም።
ይሁንና ይሄ እስከ መጨረሻው የሚፀና ውሳኔ ላይሆን ይችላል። ምክንያቱም ይሄኛው ውጤት ይፋ ከሆነ በኋላ AIU ወደኋላ ተመልሶ በአትሌቷ ላይ ተጨማሪ ምርመራዎችን ጀምሯል።
ለምሳሌ በምርመራው ወቅት ቃለ-ምልልስ ሲደረግላት "ባመመኝ ሰዓት ይሄንን ሀይድሮክሎራይዝድ ጨምሮ ሌሎችንም የባህል መድሃኒቶችን የምትሰጠኝ የቤት ሰራተኛዬ ናት" የሚል ቃል ሰጥታለች። በዚህም ሰራተኛዋም ምርመራ እየተደረገባት ነው።
ቼፕንጌቲች "Rosa Associati" በተባለው የአትሌቲክስ ማኔጅመንት ስር ነው የምትወዳደረው። የዚህ ኩባንያ ባለቤት ጣልያናዊው ፌዴሪኮ ሮሳ (በ2ኛው ፎቶ የሚታየው) ነው።
ይህ ሰው ከ30 በላይ ስመጥር ኬንያውያን አትሌቶችን በስሩ የሚያስተዳድር ሲሆን ከዶፒንግ ጋር በተያያዘ ለቅጣት ከሚዳረጉት በርካታ የሀገሪቱ አትሌቶች መካከልም አብዛኛዎቹ በእሱ ስር የሚወዳደሩ ናቸው። የኬንያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ከኦገስት 2025 አንስቶ እገዳ ጥሎበታል። ይህንን ተከትሎም እሱም በAIU ምርመራ እየተደረገበት ነው።
ይህም ብቻ ሳይሆን የቼፕንጌቲች የሞባይል ስልክ ላይም ምርመራ እየተደረገ ነው። አትሌቷ መጀመሪያ ላይ ሞባይሏን ላለማስፈተሽ አንገራግራ የነበረ ቢሆንም በኋላ ላይ ግን ተስማምታለች። ከፌዴሪኮ ሮሳ ጋር የተፃፃፈቻቸው መልዕክቶች እና የመድሃኒት ፎቶዎች እየተመረመሩ ነው።
የእነዚህ ምርመራ ገና በሂደት ላይ ነው። ወደ ኋላ ተሂዶ እየተደረገ ባለው ምርመራና የመጨረሻ ውጤት ከዚህ በፊትም ዶፒንግ ትወስድ እንደነበር ከተረጋገጠባት ሪከርዱን ልትነጠቅና ለትዕግስት አሰፋ ሊመለስላት ይችላል።
11 months ago
ኤምባሲው በቱሪስት ቪዛ ሕጻናት ለመውለድ ወደ አሜሪካ የሚጓዙ ኢትዮጵያዊያንን አሳሰበ
በኢትዮጵያ የአሜሪካ ኤምባሲ በቱሪስት ቪዛ ሕጻናት ለመውለድ ወደ አሜሪካ የሚጓዙ ኢትዮጵያዊያንን አስመልክቶ ማሳሰቢያ አውጥቷል።
በማሳሰቢያውም በርካታ የቱሪስት ቪዛ ያላቸው ወላጆች ለመውለድ ዓላማ ወደ አሜሪካ እንደሚጓዙ የገለጸ ሲሆን፤ በዛም ለሕክምና እንክብካቤ ወጪያቸው የመንግሥትን የገንዘብ ድጋፍ (ሜዲኬይድ) ይጠቀማሉ ብሏል።
እነዚህም ወጪዎች በዋናነት ወደ የአሜሪካን ግብር ከፋዮች እንደሚተላለፋ የገለጸው ኤምባሲው፤ ይህም ዜጎችን ለከፍተኛ ወጪ የሚዳርግ መሆኑን አስታውቋል።
እንዲሁም በዚህ መንገድ ወደ ሀገሪቱ የገቡ ዜጎች ለወደ ፊት የአሜሪካ ቪዛ ለማደስ በሚያመለክቱበት ወቅት፤ ቪዛቸው ተቀባይነት ሊኖረው እንደማይችል አመላክቷል።
በመሆኑም በቱሪስት ቪዛ ወደ አሜሪካ ለመጓዝ የሚያስቡ ኢትዮጵያውያን ዜጎች፤ ይህንን ማሳሰቢያ በአጽንኦት በመመልከት የቪዛውን ትክክለኛ ዓላማ እንዲያከብሩ እና ለጉዞአቸው ተገቢውን የቪዛ አይነት እንዲጠይቁ ማሳሰቢያ አስተላልፏል።
የአሜሪካ መንግሥት ባለፉት በርካታ ወራት የሀገሪቷን ደህንነት ለማስጠበቅ እንዲሁም፤ የሌላ ሀገራት ዜጎችን እንቅስቃሴ ለማጥበቅ ያቀዱ በርካታ ተከታታይ እርምጃዎችን በመውሰድ ላይ ይገኛል።
ከእነዚህም ጉልህ ለውጦች መካከል የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር እ.ኤ.አ ከመስከረም 6 ቀን 2025 ጀምሮ ተግባራዊ ያደረገው አዲስ ሕግ አንዱ ሲሆን፤ ይህም ለአጭር ጊዜ የሚያገለግሉ የቪዛ ማመልከቻዎች አመልካች በሚኖሩበት የዜግነት ሀገር መቅረብ እንዳለባቸው የሚያስገድድ ነው።
ሌላው ደግሞ የቱሪስት ቪዛ (B-1/B-2) አመልካቾችን የተመለከተው የቪዛ ፕሮግራም ሲሆን፤ የአሜሪካ ቆንስላ ባለስልጣናት በቀጣይ የቱሪስት ቪዛ በማግኘት ወደ ሀገሪቱ ለሚገቡ ግለሰቦች ተመላሽ የሚሆን የ5 ሺሕ፣ 10 ሺሕ ወይም የ15 ሺሕ ዶላር ማስያዣ ሊጠይቁ ይችላሉ ተብሏል፡፡
ይህም ተጓዡ የሚቆይበትን ሁኔታ ሙሉ በሙሉ ካሟላ ብቻ የሚመለስ መሆኑ የተገለጸ ሲሆን፤ ለአሁኑ ይህ እርምጃ የማላዊ እና የዛምቢያ ዜጎች ላይ ብቻ ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል።
በተጨማሪም፣ ምናልባት ከቀጣይ ወር መጀመሪያ አንስቶ የአሜሪካ መንግሥት ለአብዛኛዎቹ የአጭር ጊዜ የቪዛ ማመልከቻዎች 250 ዶላር አዲስ የቪዛ ታማኝነት ክፍያ (visa integrity fee) ያስተዋውቃል ተብሎ ይጠበቃል።
#አሐዱ
በኢትዮጵያ የአሜሪካ ኤምባሲ በቱሪስት ቪዛ ሕጻናት ለመውለድ ወደ አሜሪካ የሚጓዙ ኢትዮጵያዊያንን አስመልክቶ ማሳሰቢያ አውጥቷል።
በማሳሰቢያውም በርካታ የቱሪስት ቪዛ ያላቸው ወላጆች ለመውለድ ዓላማ ወደ አሜሪካ እንደሚጓዙ የገለጸ ሲሆን፤ በዛም ለሕክምና እንክብካቤ ወጪያቸው የመንግሥትን የገንዘብ ድጋፍ (ሜዲኬይድ) ይጠቀማሉ ብሏል።
እነዚህም ወጪዎች በዋናነት ወደ የአሜሪካን ግብር ከፋዮች እንደሚተላለፋ የገለጸው ኤምባሲው፤ ይህም ዜጎችን ለከፍተኛ ወጪ የሚዳርግ መሆኑን አስታውቋል።
እንዲሁም በዚህ መንገድ ወደ ሀገሪቱ የገቡ ዜጎች ለወደ ፊት የአሜሪካ ቪዛ ለማደስ በሚያመለክቱበት ወቅት፤ ቪዛቸው ተቀባይነት ሊኖረው እንደማይችል አመላክቷል።
በመሆኑም በቱሪስት ቪዛ ወደ አሜሪካ ለመጓዝ የሚያስቡ ኢትዮጵያውያን ዜጎች፤ ይህንን ማሳሰቢያ በአጽንኦት በመመልከት የቪዛውን ትክክለኛ ዓላማ እንዲያከብሩ እና ለጉዞአቸው ተገቢውን የቪዛ አይነት እንዲጠይቁ ማሳሰቢያ አስተላልፏል።
የአሜሪካ መንግሥት ባለፉት በርካታ ወራት የሀገሪቷን ደህንነት ለማስጠበቅ እንዲሁም፤ የሌላ ሀገራት ዜጎችን እንቅስቃሴ ለማጥበቅ ያቀዱ በርካታ ተከታታይ እርምጃዎችን በመውሰድ ላይ ይገኛል።
ከእነዚህም ጉልህ ለውጦች መካከል የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር እ.ኤ.አ ከመስከረም 6 ቀን 2025 ጀምሮ ተግባራዊ ያደረገው አዲስ ሕግ አንዱ ሲሆን፤ ይህም ለአጭር ጊዜ የሚያገለግሉ የቪዛ ማመልከቻዎች አመልካች በሚኖሩበት የዜግነት ሀገር መቅረብ እንዳለባቸው የሚያስገድድ ነው።
ሌላው ደግሞ የቱሪስት ቪዛ (B-1/B-2) አመልካቾችን የተመለከተው የቪዛ ፕሮግራም ሲሆን፤ የአሜሪካ ቆንስላ ባለስልጣናት በቀጣይ የቱሪስት ቪዛ በማግኘት ወደ ሀገሪቱ ለሚገቡ ግለሰቦች ተመላሽ የሚሆን የ5 ሺሕ፣ 10 ሺሕ ወይም የ15 ሺሕ ዶላር ማስያዣ ሊጠይቁ ይችላሉ ተብሏል፡፡
ይህም ተጓዡ የሚቆይበትን ሁኔታ ሙሉ በሙሉ ካሟላ ብቻ የሚመለስ መሆኑ የተገለጸ ሲሆን፤ ለአሁኑ ይህ እርምጃ የማላዊ እና የዛምቢያ ዜጎች ላይ ብቻ ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል።
በተጨማሪም፣ ምናልባት ከቀጣይ ወር መጀመሪያ አንስቶ የአሜሪካ መንግሥት ለአብዛኛዎቹ የአጭር ጊዜ የቪዛ ማመልከቻዎች 250 ዶላር አዲስ የቪዛ ታማኝነት ክፍያ (visa integrity fee) ያስተዋውቃል ተብሎ ይጠበቃል።
#አሐዱ
11 months ago
ኤምባሲው በቱሪስት ቪዛ ሕጻናት ለመውለድ ወደ አሜሪካ የሚጓዙ ኢትዮጵያዊያንን አሳሰበ
በኢትዮጵያ የአሜሪካ ኤምባሲ በቱሪስት ቪዛ ሕጻናት ለመውለድ ወደ አሜሪካ የሚጓዙ ኢትዮጵያዊያንን አስመልክቶ ማሳሰቢያ አውጥቷል።
በማሳሰቢያውም በርካታ የቱሪስት ቪዛ ያላቸው ወላጆች ለመውለድ ዓላማ ወደ አሜሪካ እንደሚጓዙ የገለጸ ሲሆን፤ በዛም ለሕክምና እንክብካቤ ወጪያቸው የመንግሥትን የገንዘብ ድጋፍ (ሜዲኬይድ) ይጠቀማሉ ብሏል።
እነዚህም ወጪዎች በዋናነት ወደ የአሜሪካን ግብር ከፋዮች እንደሚተላለፋ የገለጸው ኤምባሲው፤ ይህም ዜጎችን ለከፍተኛ ወጪ የሚዳርግ መሆኑን አስታውቋል።
እንዲሁም በዚህ መንገድ ወደ ሀገሪቱ የገቡ ዜጎች ለወደ ፊት የአሜሪካ ቪዛ ለማደስ በሚያመለክቱበት ወቅት፤ ቪዛቸው ተቀባይነት ሊኖረው እንደማይችል አመላክቷል።
በመሆኑም በቱሪስት ቪዛ ወደ አሜሪካ ለመጓዝ የሚያስቡ ኢትዮጵያውያን ዜጎች፤ ይህንን ማሳሰቢያ በአጽንኦት በመመልከት የቪዛውን ትክክለኛ ዓላማ እንዲያከብሩ እና ለጉዞአቸው ተገቢውን የቪዛ አይነት እንዲጠይቁ ማሳሰቢያ አስተላልፏል።
የአሜሪካ መንግሥት ባለፉት በርካታ ወራት የሀገሪቷን ደህንነት ለማስጠበቅ እንዲሁም፤ የሌላ ሀገራት ዜጎችን እንቅስቃሴ ለማጥበቅ ያቀዱ በርካታ ተከታታይ እርምጃዎችን በመውሰድ ላይ ይገኛል።
ከእነዚህም ጉልህ ለውጦች መካከል የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር እ.ኤ.አ ከመስከረም 6 ቀን 2025 ጀምሮ ተግባራዊ ያደረገው አዲስ ሕግ አንዱ ሲሆን፤ ይህም ለአጭር ጊዜ የሚያገለግሉ የቪዛ ማመልከቻዎች አመልካች በሚኖሩበት የዜግነት ሀገር መቅረብ እንዳለባቸው የሚያስገድድ ነው።
ሌላው ደግሞ የቱሪስት ቪዛ (B-1/B-2) አመልካቾችን የተመለከተው የቪዛ ፕሮግራም ሲሆን፤ የአሜሪካ ቆንስላ ባለስልጣናት በቀጣይ የቱሪስት ቪዛ በማግኘት ወደ ሀገሪቱ ለሚገቡ ግለሰቦች ተመላሽ የሚሆን የ5 ሺሕ፣ 10 ሺሕ ወይም የ15 ሺሕ ዶላር ማስያዣ ሊጠይቁ ይችላሉ ተብሏል፡፡
ይህም ተጓዡ የሚቆይበትን ሁኔታ ሙሉ በሙሉ ካሟላ ብቻ የሚመለስ መሆኑ የተገለጸ ሲሆን፤ ለአሁኑ ይህ እርምጃ የማላዊ እና የዛምቢያ ዜጎች ላይ ብቻ ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል።
በተጨማሪም፣ ምናልባት ከቀጣይ ወር መጀመሪያ አንስቶ የአሜሪካ መንግሥት ለአብዛኛዎቹ የአጭር ጊዜ የቪዛ ማመልከቻዎች 250 ዶላር አዲስ የቪዛ ታማኝነት ክፍያ (visa integrity fee) ያስተዋውቃል ተብሎ ይጠበቃል።
አሐዱ
በኢትዮጵያ የአሜሪካ ኤምባሲ በቱሪስት ቪዛ ሕጻናት ለመውለድ ወደ አሜሪካ የሚጓዙ ኢትዮጵያዊያንን አስመልክቶ ማሳሰቢያ አውጥቷል።
በማሳሰቢያውም በርካታ የቱሪስት ቪዛ ያላቸው ወላጆች ለመውለድ ዓላማ ወደ አሜሪካ እንደሚጓዙ የገለጸ ሲሆን፤ በዛም ለሕክምና እንክብካቤ ወጪያቸው የመንግሥትን የገንዘብ ድጋፍ (ሜዲኬይድ) ይጠቀማሉ ብሏል።
እነዚህም ወጪዎች በዋናነት ወደ የአሜሪካን ግብር ከፋዮች እንደሚተላለፋ የገለጸው ኤምባሲው፤ ይህም ዜጎችን ለከፍተኛ ወጪ የሚዳርግ መሆኑን አስታውቋል።
እንዲሁም በዚህ መንገድ ወደ ሀገሪቱ የገቡ ዜጎች ለወደ ፊት የአሜሪካ ቪዛ ለማደስ በሚያመለክቱበት ወቅት፤ ቪዛቸው ተቀባይነት ሊኖረው እንደማይችል አመላክቷል።
በመሆኑም በቱሪስት ቪዛ ወደ አሜሪካ ለመጓዝ የሚያስቡ ኢትዮጵያውያን ዜጎች፤ ይህንን ማሳሰቢያ በአጽንኦት በመመልከት የቪዛውን ትክክለኛ ዓላማ እንዲያከብሩ እና ለጉዞአቸው ተገቢውን የቪዛ አይነት እንዲጠይቁ ማሳሰቢያ አስተላልፏል።
የአሜሪካ መንግሥት ባለፉት በርካታ ወራት የሀገሪቷን ደህንነት ለማስጠበቅ እንዲሁም፤ የሌላ ሀገራት ዜጎችን እንቅስቃሴ ለማጥበቅ ያቀዱ በርካታ ተከታታይ እርምጃዎችን በመውሰድ ላይ ይገኛል።
ከእነዚህም ጉልህ ለውጦች መካከል የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር እ.ኤ.አ ከመስከረም 6 ቀን 2025 ጀምሮ ተግባራዊ ያደረገው አዲስ ሕግ አንዱ ሲሆን፤ ይህም ለአጭር ጊዜ የሚያገለግሉ የቪዛ ማመልከቻዎች አመልካች በሚኖሩበት የዜግነት ሀገር መቅረብ እንዳለባቸው የሚያስገድድ ነው።
ሌላው ደግሞ የቱሪስት ቪዛ (B-1/B-2) አመልካቾችን የተመለከተው የቪዛ ፕሮግራም ሲሆን፤ የአሜሪካ ቆንስላ ባለስልጣናት በቀጣይ የቱሪስት ቪዛ በማግኘት ወደ ሀገሪቱ ለሚገቡ ግለሰቦች ተመላሽ የሚሆን የ5 ሺሕ፣ 10 ሺሕ ወይም የ15 ሺሕ ዶላር ማስያዣ ሊጠይቁ ይችላሉ ተብሏል፡፡
ይህም ተጓዡ የሚቆይበትን ሁኔታ ሙሉ በሙሉ ካሟላ ብቻ የሚመለስ መሆኑ የተገለጸ ሲሆን፤ ለአሁኑ ይህ እርምጃ የማላዊ እና የዛምቢያ ዜጎች ላይ ብቻ ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል።
በተጨማሪም፣ ምናልባት ከቀጣይ ወር መጀመሪያ አንስቶ የአሜሪካ መንግሥት ለአብዛኛዎቹ የአጭር ጊዜ የቪዛ ማመልከቻዎች 250 ዶላር አዲስ የቪዛ ታማኝነት ክፍያ (visa integrity fee) ያስተዋውቃል ተብሎ ይጠበቃል።
አሐዱ
Sponsored by
Surafel
11 months ago
አትሌት ድርቤ ወልተጂ ከውድድሩ ውጪ ሆነች
ኢትዮጵያን በአለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ውድድር በ 1500ሜ ለመወከል ተመርጣ የነበረችው አትሌት ድርቤ ወልተጂ ከውድድሩ ውጪ መሆኗ ተገልጿል።
አትትሌቷ ከውድድሩ ውጪ የሆነችው ሊደረግላት የነበረውን የአበረታች ንጥረነገር ምርመራ ለማድረግ ፈቃደኛ ባለመሆኗ መሆኑ ተነግሯል።
አትሌቶች አበረታች ዕፅ መጠቀም አለመጠቀማቸውን የሚቆጣጠረው "The Athletics Integrity Unit (AIU)" የዶፒንግ ምርመራ እንድትሰጥ ቢጠይቃትም ፈቃደኛ አለመሆኗ ተገልጿል።
ይህንንም ተከትሎ " AIU " አትሌቷ ከቶኪዮው የዓለም ሻምፒዮና ውጪ እንድትሆን ለዓለም አቀፉ የስፖርት ጉዳዮች ግልግል ችሎት (Court of Arbitration for Sport (CAS) ክስ አቅርቧል።
የክሱ ውሳኔው በዓለም አቀፉ የስፖርት ጉዳዮች ግልግል ችሎት የታወቀ ሲሆን አትሌት ድርቤ ወልተጂ ከውድድሩ ውጪ መሆኗ ታውቋል።
በርቀቱ ሁለተኛ ምርጥ ሰዓት ባለቤት የሆነችው አትሌቷ ለኢትዮጵያ ሜዳልያ ያስገኛሉ ተብለው ከሚጠበቁ አትሌቶች አንዷ ነበረች።
ምንጭ :- ጋዜጠኛ ብሩክ ተስፋዬ
ኢትዮጵያን በአለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ውድድር በ 1500ሜ ለመወከል ተመርጣ የነበረችው አትሌት ድርቤ ወልተጂ ከውድድሩ ውጪ መሆኗ ተገልጿል።
አትትሌቷ ከውድድሩ ውጪ የሆነችው ሊደረግላት የነበረውን የአበረታች ንጥረነገር ምርመራ ለማድረግ ፈቃደኛ ባለመሆኗ መሆኑ ተነግሯል።
አትሌቶች አበረታች ዕፅ መጠቀም አለመጠቀማቸውን የሚቆጣጠረው "The Athletics Integrity Unit (AIU)" የዶፒንግ ምርመራ እንድትሰጥ ቢጠይቃትም ፈቃደኛ አለመሆኗ ተገልጿል።
ይህንንም ተከትሎ " AIU " አትሌቷ ከቶኪዮው የዓለም ሻምፒዮና ውጪ እንድትሆን ለዓለም አቀፉ የስፖርት ጉዳዮች ግልግል ችሎት (Court of Arbitration for Sport (CAS) ክስ አቅርቧል።
የክሱ ውሳኔው በዓለም አቀፉ የስፖርት ጉዳዮች ግልግል ችሎት የታወቀ ሲሆን አትሌት ድርቤ ወልተጂ ከውድድሩ ውጪ መሆኗ ታውቋል።
በርቀቱ ሁለተኛ ምርጥ ሰዓት ባለቤት የሆነችው አትሌቷ ለኢትዮጵያ ሜዳልያ ያስገኛሉ ተብለው ከሚጠበቁ አትሌቶች አንዷ ነበረች።
ምንጭ :- ጋዜጠኛ ብሩክ ተስፋዬ
1 year ago
ለዩኒቨርሲቲ መምህሩ አስናቀ ብርሃኑ እንድረስለት
Lets support Our Teacher
Yilkal Andualem is organizing this fundraiser.
Donation protected
መምህራችን_ታሞብናል
ወደ ካንሰር ሊቀየር ይችላል....ሀኪሞች
ወጣት መ/ር አስናቀ ብርሃኑ አላምነህ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ በቅንነትና በታማኝነት እያገለገለ ያለ በሙያውም አንቱታን ያተረፈ በሥነ ምግባሩ ምስጉን ሰው አክባሪ፣ ለተቸገሩ ፈጥኖ ደራሽ ወንድማችን ነው::
በሒሳብ ትምህርት ክፍል የኑሜሪካል አናላይሲስ መምህር ሲሆን በዩኒቨርሲቲ ቆይታውም ከማስተማር ስራው ጎን ለጎን በጥናትና ምርምር ዘርፍ በሙያው አለም አቀፍ ተቀባይነት ያላቸው 6 (ስድስት) ጥናትና ምርምሮችን በማሳተም ለአንባቢያን አድርሷል::
ወንድማችን መ/ር አስናቀ ድንገት በገጠመው የጤና እክል በህይወት እና በሞት መካከል ሆኖ የድረሱልኝ ተማፅኖውን እያሰማ ይገኛል:: በገጠመው የጤና ዕክል በተለያዩ ስድስት (6) ሆስፒታሎች ህክምና ሲያደርግ ቆይቷል::
ከነዚህም ውስጥ በአንዱ ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ሆስፒታል ሰርጀሪ ተሰርቶ ሊሻለው ባለመቻሉ ወደ አዲስ አበባ አለርት ኮምፕርሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ሪፈር ተፅፎለት ክትትል እያደረገ ይገኛል::
በመሆኑም የአለርት ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የህክምና ቦርድ 30% አጠቃላይ ቋሚ የአካል ጉዳተኛ እንደሆነና የሚከተሉትን ውሳኔዎችን ወስኗል::
1ኛ. በግራ እግሩ ላይ ስድስት (6) ዓመት የቆየ ከባድ ቁስለት ወደ ካንሰር የመቀየር እድሉ እጅግ በጣም ከፍተኛ መሆኑን፣
2ኛ. ሁለቱም እግሮቹ ነርቫቸው የተጎዳና ስሜት አልባ መሆናቸውን፣
3ኛ. የግራ እግሩ ሙሉ አጥንቶቹ የተጎዱና ይዘታቸውን የቀየሩ መሆናቸውን
4ኛ. ቁሞ ማስተማርም ሆነ በእግሩ መንቀሳቀስ እንደማይችል የአለርት ሆስፒታል ሜዲካል ቦርዱ አረጋግጧል
መምህር አስናቀ ባለብዙ ተስፋና ብዙ ህልም የነበረዉ ሩጦ ያልጠገበ ወንድማችን እግሮቹ ደክመው እቤት እንዲውል ተገዷል::
የህመሙ ሁኔታ አሳሳቢ እና ለህይወቱም አስጊ ደረጃ ላይ በመድረሱ ወደ ህንድ አገር ሂዶ ህክምና እንዲያደርግ ሪፈር ተፅፎለታል:: የህክምና ወጭውም ከሁለት ሚሊየን (2,000,000) ብር በላይ እንደሚያስፈልገው ተነግሮታል::
ወንድማችንን ለማገዝ አነሰ በዛ ሳንል በአገር ውስጥና በውጭ ያላችሁ ትዉልደ ኢትዮጵያውያንና ኤርትራውያን የእርዳታ እጃችሁን ትዘርጉ ዘንድ በፈጣሪ ስም እንጠይቃለን::
Asinake Birihanu Alamneh
ስልክ_ቁጥር 09 23 53 45 01
Lecturer Asnake Berhanu, who has been serving Hawassa University with integrity and honesty, is a respected, respectful, and helpful person who has earned a reputation in his profession.
He is a Numerical Analysis Lecturer in the Department of Mathematics.
During his time at the university, he has published 6 (six) internationally recognized studies and research papers in his field, and has reached readers.
Our brother,Teacher Asnake is suddenly in the middle of life and death due to a health problem he encountered.
He has been receiving treatment in six (6) different hospitals for his health problem. In one of them, he underwent surgery at Hawassa University Referral Hospital and was referred to Addis Ababa Alert Compressive Specialized Hospital for follow-up.
Therefore, the Alert Specialized Hospital Medical Board has determined that he is 30% permanently disabled and has made the following decisions:
1st. The six (6) year old severe ulcer on his left leg has a very high chance of turning into cancer,
2nd. Both his legs are nerve damaged and numb,
3rd. The entire bones of his left leg are damaged and their contents have changed,
4th. The Alert Hospital Medical Board has confirmed that he cannot stand or walk.
Our brother, Teacher Asnake, who had many hopes and dreams, has been forced to stay home due to tired legs. His condition is serious and life-threatening, so he has been referred to India for treatment. He has been told that the medical expenses will cost more than $15000 .
Please help support this visionary teacher as they navigate through an incredibly difficult time. The funds raised will go towards the cost of surgical treatment , and to help to cover the loss of income while taking some much needed time to recover.
Thank you for your generosity.
I am grateful for your help and wishes.
Thank you
"Let's save the life of the visionary teacher with sincere hearts and united hands!
Show your support for this GoFundMe
Lets support Our Teacher
Yilkal Andualem is organizing this fundraiser.
Donation protected
መምህራችን_ታሞብናል
ወደ ካንሰር ሊቀየር ይችላል....ሀኪሞች
ወጣት መ/ር አስናቀ ብርሃኑ አላምነህ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ በቅንነትና በታማኝነት እያገለገለ ያለ በሙያውም አንቱታን ያተረፈ በሥነ ምግባሩ ምስጉን ሰው አክባሪ፣ ለተቸገሩ ፈጥኖ ደራሽ ወንድማችን ነው::
በሒሳብ ትምህርት ክፍል የኑሜሪካል አናላይሲስ መምህር ሲሆን በዩኒቨርሲቲ ቆይታውም ከማስተማር ስራው ጎን ለጎን በጥናትና ምርምር ዘርፍ በሙያው አለም አቀፍ ተቀባይነት ያላቸው 6 (ስድስት) ጥናትና ምርምሮችን በማሳተም ለአንባቢያን አድርሷል::
ወንድማችን መ/ር አስናቀ ድንገት በገጠመው የጤና እክል በህይወት እና በሞት መካከል ሆኖ የድረሱልኝ ተማፅኖውን እያሰማ ይገኛል:: በገጠመው የጤና ዕክል በተለያዩ ስድስት (6) ሆስፒታሎች ህክምና ሲያደርግ ቆይቷል::
ከነዚህም ውስጥ በአንዱ ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ሆስፒታል ሰርጀሪ ተሰርቶ ሊሻለው ባለመቻሉ ወደ አዲስ አበባ አለርት ኮምፕርሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ሪፈር ተፅፎለት ክትትል እያደረገ ይገኛል::
በመሆኑም የአለርት ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የህክምና ቦርድ 30% አጠቃላይ ቋሚ የአካል ጉዳተኛ እንደሆነና የሚከተሉትን ውሳኔዎችን ወስኗል::
1ኛ. በግራ እግሩ ላይ ስድስት (6) ዓመት የቆየ ከባድ ቁስለት ወደ ካንሰር የመቀየር እድሉ እጅግ በጣም ከፍተኛ መሆኑን፣
2ኛ. ሁለቱም እግሮቹ ነርቫቸው የተጎዳና ስሜት አልባ መሆናቸውን፣
3ኛ. የግራ እግሩ ሙሉ አጥንቶቹ የተጎዱና ይዘታቸውን የቀየሩ መሆናቸውን
4ኛ. ቁሞ ማስተማርም ሆነ በእግሩ መንቀሳቀስ እንደማይችል የአለርት ሆስፒታል ሜዲካል ቦርዱ አረጋግጧል
መምህር አስናቀ ባለብዙ ተስፋና ብዙ ህልም የነበረዉ ሩጦ ያልጠገበ ወንድማችን እግሮቹ ደክመው እቤት እንዲውል ተገዷል::
የህመሙ ሁኔታ አሳሳቢ እና ለህይወቱም አስጊ ደረጃ ላይ በመድረሱ ወደ ህንድ አገር ሂዶ ህክምና እንዲያደርግ ሪፈር ተፅፎለታል:: የህክምና ወጭውም ከሁለት ሚሊየን (2,000,000) ብር በላይ እንደሚያስፈልገው ተነግሮታል::
ወንድማችንን ለማገዝ አነሰ በዛ ሳንል በአገር ውስጥና በውጭ ያላችሁ ትዉልደ ኢትዮጵያውያንና ኤርትራውያን የእርዳታ እጃችሁን ትዘርጉ ዘንድ በፈጣሪ ስም እንጠይቃለን::
Asinake Birihanu Alamneh
ስልክ_ቁጥር 09 23 53 45 01
Lecturer Asnake Berhanu, who has been serving Hawassa University with integrity and honesty, is a respected, respectful, and helpful person who has earned a reputation in his profession.
He is a Numerical Analysis Lecturer in the Department of Mathematics.
During his time at the university, he has published 6 (six) internationally recognized studies and research papers in his field, and has reached readers.
Our brother,Teacher Asnake is suddenly in the middle of life and death due to a health problem he encountered.
He has been receiving treatment in six (6) different hospitals for his health problem. In one of them, he underwent surgery at Hawassa University Referral Hospital and was referred to Addis Ababa Alert Compressive Specialized Hospital for follow-up.
Therefore, the Alert Specialized Hospital Medical Board has determined that he is 30% permanently disabled and has made the following decisions:
1st. The six (6) year old severe ulcer on his left leg has a very high chance of turning into cancer,
2nd. Both his legs are nerve damaged and numb,
3rd. The entire bones of his left leg are damaged and their contents have changed,
4th. The Alert Hospital Medical Board has confirmed that he cannot stand or walk.
Our brother, Teacher Asnake, who had many hopes and dreams, has been forced to stay home due to tired legs. His condition is serious and life-threatening, so he has been referred to India for treatment. He has been told that the medical expenses will cost more than $15000 .
Please help support this visionary teacher as they navigate through an incredibly difficult time. The funds raised will go towards the cost of surgical treatment , and to help to cover the loss of income while taking some much needed time to recover.
Thank you for your generosity.
I am grateful for your help and wishes.
Thank you
"Let's save the life of the visionary teacher with sincere hearts and united hands!
Show your support for this GoFundMe
Comments