5 hours ago
ጤና ልማትና ፀረ‐ወባ ማህበር በአማርኛ የተዘጋጀ የመጀመሪያውን የትምባሆ ቁጥጥር ዲጂታል ዳሽቦርድ ይፋ አደረገ!
#fastmereja :-በኢትዮጵያ በትምባሆ ቁጥጥር ዙሪያ ያሉ የተበታተኑ መረጃዎችን በአንድ ማዕከል ለማደራጀትና ተደራሽነታቸውን ለማስፋት ያለመው «የትምባሆ ቁጥጥርዳታ ኢኒሺዬቲቭ» (TCDI Ethiopia) ዳሽቦርድ፣ የአማርኛ ገጾቹን በይዘት በማበልፀግ በዛሬው ዕለት በይፋ ተመረቀ።
ይህ አገራዊ የዲጂታል ዳሽቦርድ ይፋ የተደረገው የጤና፣ ልማት እና ፀረ-ወባ ማህበር (HDAMA) ከኢትዮጵያ ምግብ እና መድኃኒት ባለሥልጣን (EFDA) ጋር በመተባበር ባዘጋጁት ልዩ የመክፈቻ መርሃ-ግብር ላይ ነው፡፡
የዳሽቦርዱ በይፋ መከፈት በኢትዮጵያ የትምባሆ ቁጥጥር ፖሊሲዎችን፣ ስትራቴጂዎችን እና ሕጋዊ ውሳኔዎችን ሙሉ በሙሉ በምርምርና በፅኑ መረጃ (Data-driven decision making) ላይ የተመሰረቱ ለማድረግ ትልቅ አቅም እንደሚፈጥር ተገልጿል።
ቀደም ሲል በተለያዩ ተቋማት እና ተመራማሪዎች ዘንድ ተበታትነው ይገኙ የነበሩ መረጃዎች በአንድ ቋት መደራጀታቸው፣ ፖሊሲ አውጪዎችና የሕብረተሰብ ጤና ባለሙያዎች ትክክለኛ አገራዊ ስታቲስቲክሶችን በመጠቀም ፈጣንና ውጤታማ እርምጃዎችን እንዲወስዱ እንደሚያስችላቸዉ ተገልጿል።
የቋንቋ ተደራሽነትና የባለድርሻ አካላት ምክክር የዳሽቦርዱ ገጾች በአማርኛ ቋንቋ ተበልፅገው መቅረባቸው የመረጃ ተደራሽነትን ከመጨመሩ ባለፈ፣ ለመገናኛ ብዙኃን፣ ለተመራማሪዎችና ለመላው ህብረተሰብ የግንዛቤ ማሳደጊያ ቁልፍ መሳሪያ ሆኖ እንደሚያገለግል ታውቋል።
በማስጀመርያ ስነ-ስርዓቱ ላይ የተገኙት የየዘርፉ ባለድርሻ አካላት የዳሽቦርዱን መመረቅ ተከትሎ በስፋት ዉይይት የተካሄደባቸዉ ሲሆን በውይይቱም ዳሽቦርዱ የሚያቀርባቸውን ዳታዎች ለሕግና ፖሊሲ ማሻሻያ አግባብነት ባለው መልኩ ጥቅም ላይ ማዋል በሚቻልበት ሁኔታ ላይ አስተያየቶችን ተለዋውጠዋል።
ይህንን ጠቃሚ ዳሽቦርድ ወደ አማርኛ በመተርጎም፣ በማበልፀግ እና ለዛሬው ማስተዋወቂያ መድረክ የቴክኒክና የመረጃ ማዕከል ድጋፍ ላደረጉት የኢትዮጵያ የምግብ እና መድኃኒት ባለስልጣን፣ HDAMA፣ Development Gateway (DG) A Center for the Study of the Economies of Africa (CSEA) እንዲሁም ለሌሎች አጋር አካላት ምስጋና ቀርቧል።
#fastmereja :-በኢትዮጵያ በትምባሆ ቁጥጥር ዙሪያ ያሉ የተበታተኑ መረጃዎችን በአንድ ማዕከል ለማደራጀትና ተደራሽነታቸውን ለማስፋት ያለመው «የትምባሆ ቁጥጥርዳታ ኢኒሺዬቲቭ» (TCDI Ethiopia) ዳሽቦርድ፣ የአማርኛ ገጾቹን በይዘት በማበልፀግ በዛሬው ዕለት በይፋ ተመረቀ።
ይህ አገራዊ የዲጂታል ዳሽቦርድ ይፋ የተደረገው የጤና፣ ልማት እና ፀረ-ወባ ማህበር (HDAMA) ከኢትዮጵያ ምግብ እና መድኃኒት ባለሥልጣን (EFDA) ጋር በመተባበር ባዘጋጁት ልዩ የመክፈቻ መርሃ-ግብር ላይ ነው፡፡
የዳሽቦርዱ በይፋ መከፈት በኢትዮጵያ የትምባሆ ቁጥጥር ፖሊሲዎችን፣ ስትራቴጂዎችን እና ሕጋዊ ውሳኔዎችን ሙሉ በሙሉ በምርምርና በፅኑ መረጃ (Data-driven decision making) ላይ የተመሰረቱ ለማድረግ ትልቅ አቅም እንደሚፈጥር ተገልጿል።
ቀደም ሲል በተለያዩ ተቋማት እና ተመራማሪዎች ዘንድ ተበታትነው ይገኙ የነበሩ መረጃዎች በአንድ ቋት መደራጀታቸው፣ ፖሊሲ አውጪዎችና የሕብረተሰብ ጤና ባለሙያዎች ትክክለኛ አገራዊ ስታቲስቲክሶችን በመጠቀም ፈጣንና ውጤታማ እርምጃዎችን እንዲወስዱ እንደሚያስችላቸዉ ተገልጿል።
የቋንቋ ተደራሽነትና የባለድርሻ አካላት ምክክር የዳሽቦርዱ ገጾች በአማርኛ ቋንቋ ተበልፅገው መቅረባቸው የመረጃ ተደራሽነትን ከመጨመሩ ባለፈ፣ ለመገናኛ ብዙኃን፣ ለተመራማሪዎችና ለመላው ህብረተሰብ የግንዛቤ ማሳደጊያ ቁልፍ መሳሪያ ሆኖ እንደሚያገለግል ታውቋል።
በማስጀመርያ ስነ-ስርዓቱ ላይ የተገኙት የየዘርፉ ባለድርሻ አካላት የዳሽቦርዱን መመረቅ ተከትሎ በስፋት ዉይይት የተካሄደባቸዉ ሲሆን በውይይቱም ዳሽቦርዱ የሚያቀርባቸውን ዳታዎች ለሕግና ፖሊሲ ማሻሻያ አግባብነት ባለው መልኩ ጥቅም ላይ ማዋል በሚቻልበት ሁኔታ ላይ አስተያየቶችን ተለዋውጠዋል።
ይህንን ጠቃሚ ዳሽቦርድ ወደ አማርኛ በመተርጎም፣ በማበልፀግ እና ለዛሬው ማስተዋወቂያ መድረክ የቴክኒክና የመረጃ ማዕከል ድጋፍ ላደረጉት የኢትዮጵያ የምግብ እና መድኃኒት ባለስልጣን፣ HDAMA፣ Development Gateway (DG) A Center for the Study of the Economies of Africa (CSEA) እንዲሁም ለሌሎች አጋር አካላት ምስጋና ቀርቧል።
10 hours ago
የስንዴ ወፍጮ ቤት ሰርተው ልጃቸውን ለቁም ነገር ያበቁ ለዳውን ሲንድረም የተጋለጡ አባት
#ethiopia | የዳውን ሲንድረም ያለባቸው ሰዎች ልጅ ማሳደግ አይችሉም የሚለውን የተሳሳተ አመለካከት በመስበር በሶሪያ የሚኖሩት አባት ጃድ ኢሳ ሁሉን የሚያስተምር ታሪክ አስመዝግበዋል።
በስንዴ ወፍጮ ቤት ውስጥ ጠንክረው በመስራት ብቸኛ ልጃቸውን ሳደር ኢሳን በፍቅር፣ በእንክብካቤ እና በሙሉ ድጋፍ ያሳደጉት አባቱ፣ ለልጃቸው የትምህርት ስኬት ትልቅ መሠረት ሆነዋል።
የአባታቱ የማይወላወል ፍቅርና የሥራ ትጋት ብርታት የሆነው ሳደር በትምህርቱ ጠንክሮ በመማር የጥርስ ሐኪም መሆን ችሏል።
የወጣቱ ዶክተር አባት በታላቅ ኩራት "ልጄ ዶክተር ነው" ብለው በየቦታው እንዲናገሩ ሲሆን ፣የጃድና የሳደር ታሪክ እውነተኛ ወላጅነት የሚለካው በፍቅር፣ በመስዋዕትነትና በፅናት እንጂ በቅድመ-ግምት ወይም በጤና ሁኔታ አለመሆኑን ለዓለም ማሳያ ሆኗል።
በያፌት ገ/ህይወት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#ethiopia | የዳውን ሲንድረም ያለባቸው ሰዎች ልጅ ማሳደግ አይችሉም የሚለውን የተሳሳተ አመለካከት በመስበር በሶሪያ የሚኖሩት አባት ጃድ ኢሳ ሁሉን የሚያስተምር ታሪክ አስመዝግበዋል።
በስንዴ ወፍጮ ቤት ውስጥ ጠንክረው በመስራት ብቸኛ ልጃቸውን ሳደር ኢሳን በፍቅር፣ በእንክብካቤ እና በሙሉ ድጋፍ ያሳደጉት አባቱ፣ ለልጃቸው የትምህርት ስኬት ትልቅ መሠረት ሆነዋል።
የአባታቱ የማይወላወል ፍቅርና የሥራ ትጋት ብርታት የሆነው ሳደር በትምህርቱ ጠንክሮ በመማር የጥርስ ሐኪም መሆን ችሏል።
የወጣቱ ዶክተር አባት በታላቅ ኩራት "ልጄ ዶክተር ነው" ብለው በየቦታው እንዲናገሩ ሲሆን ፣የጃድና የሳደር ታሪክ እውነተኛ ወላጅነት የሚለካው በፍቅር፣ በመስዋዕትነትና በፅናት እንጂ በቅድመ-ግምት ወይም በጤና ሁኔታ አለመሆኑን ለዓለም ማሳያ ሆኗል።
በያፌት ገ/ህይወት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
13 hours ago
በጡረታ የተገለሉት አመራር ከፍተኛ ስልጣን ተሰጣቸው
*የቀድሞ የባህር ሀይሏ አመራሯ ጥቁር አሜሪካዊት ቁልፉን ተቋም ለመመራት ተሹመዋል።
#ethiopia |የአሜሪካ ሴኔት ባደረገው ምርጫ የቀድሞ የባህር ኃይል አባሏ
ዶ/ር ኤሪካ ሸዋርትዝ የአሜሪካ የበሽታዎች መከላከል እና መቆጣጠሪያ ማዕከል ዋና ዳይሬክተር አድርጎ መረጠ።
ይህ ሹመት ተቋሙ ላለፈው አንድ አመት ገደማ ያህል ያለ ቋሚ መሪ በጊዜያዊ አመራር ሲመራ ከቆየ በኋላ የተሰጠ ትልቁ ሹመት ነው ተብሏል።
የቀድሞ የባህር ሀይል አባል ዶክተር ኤሪካ በታሪክ ሲ.ዲ.ሲን በመሪነት የሚያገለግሉ የመጀመርያዋ ጥቁር አሜሪካዊት ሴት አድርጓቸዋል።
ዶክተር ኤሪካ በጡረታ የተገለሉ የባህር ኃይል አመራር የነበሩ ሲሆን ቀደም ሲል የአሜሪካ የባህር ሀይል የጤና ስርዓትን በበላይነት የመሩ ብቁ የህክምና እና የአመራር ባለሙያ መሆናቸው ታውቋል።
ላለፉት 12 ወራት ያህል ቋሚ ዳይሬክተር ሳይኖረው የቆየው ሲዲሲ ለተደቀኑበት ዓለም አቀፍ እና ሀገር አቀፍ የጤና ስጋቶች አዲስ እና ጠንካራ አመራር ለማግኘት ያደረገው ጥረት በመጨረሻም ውጤት አምጥቶለታል።
ሔኖክ ወ/ገብርኤል
#ethiopia #getutemesgen #getunews #usa #cdc #uscoastguard #drericaschwartz
*የቀድሞ የባህር ሀይሏ አመራሯ ጥቁር አሜሪካዊት ቁልፉን ተቋም ለመመራት ተሹመዋል።
#ethiopia |የአሜሪካ ሴኔት ባደረገው ምርጫ የቀድሞ የባህር ኃይል አባሏ
ዶ/ር ኤሪካ ሸዋርትዝ የአሜሪካ የበሽታዎች መከላከል እና መቆጣጠሪያ ማዕከል ዋና ዳይሬክተር አድርጎ መረጠ።
ይህ ሹመት ተቋሙ ላለፈው አንድ አመት ገደማ ያህል ያለ ቋሚ መሪ በጊዜያዊ አመራር ሲመራ ከቆየ በኋላ የተሰጠ ትልቁ ሹመት ነው ተብሏል።
የቀድሞ የባህር ሀይል አባል ዶክተር ኤሪካ በታሪክ ሲ.ዲ.ሲን በመሪነት የሚያገለግሉ የመጀመርያዋ ጥቁር አሜሪካዊት ሴት አድርጓቸዋል።
ዶክተር ኤሪካ በጡረታ የተገለሉ የባህር ኃይል አመራር የነበሩ ሲሆን ቀደም ሲል የአሜሪካ የባህር ሀይል የጤና ስርዓትን በበላይነት የመሩ ብቁ የህክምና እና የአመራር ባለሙያ መሆናቸው ታውቋል።
ላለፉት 12 ወራት ያህል ቋሚ ዳይሬክተር ሳይኖረው የቆየው ሲዲሲ ለተደቀኑበት ዓለም አቀፍ እና ሀገር አቀፍ የጤና ስጋቶች አዲስ እና ጠንካራ አመራር ለማግኘት ያደረገው ጥረት በመጨረሻም ውጤት አምጥቶለታል።
ሔኖክ ወ/ገብርኤል
#ethiopia #getutemesgen #getunews #usa #cdc #uscoastguard #drericaschwartz
16 hours ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም በአማራ ክልል፣ ፃድቃኔ ማርያም ገዳም አቅራቢያ በተከሰተው አውዳሚ የመሬት መንሸራተት አደጋ የቤተሰቦቻቸውን እና ወዳጅ ዘመዶቻቸውን ላጡ ወገኖች የተሰማቸውን ጥልቅ ሀዘን ገልጸዋል።
ዶ/ር ቴድሮስ በይፋዊ ኤክስ ገጻቸው ባሰፈሩት አጭር መልእክት፣ አደጋው የደረሰበትን ታሪካዊ ገዳም እና የአካባቢውን ቀጠና ከዚህ ቀደም በተደጋጋሚ ጊዜያት መጎብኘታቸውን አስታውሰዋል።
በአደጋው የደረሰውን ጉዳት አስመልክተውም "ለብዙዎች ጥልቅ ትርጉም ባለው በዚህ ስፍራ ላይ የደረሰውን ውድመት ማየት እጅግ ያሳዝናል" ሲሉ የተሰማቸውን ጥልቅ ሀዘን እና የልብ ስብራት አጋርተዋል።
ዶ/ር ቴድሮስ በይፋዊ ኤክስ ገጻቸው ባሰፈሩት አጭር መልእክት፣ አደጋው የደረሰበትን ታሪካዊ ገዳም እና የአካባቢውን ቀጠና ከዚህ ቀደም በተደጋጋሚ ጊዜያት መጎብኘታቸውን አስታውሰዋል።
በአደጋው የደረሰውን ጉዳት አስመልክተውም "ለብዙዎች ጥልቅ ትርጉም ባለው በዚህ ስፍራ ላይ የደረሰውን ውድመት ማየት እጅግ ያሳዝናል" ሲሉ የተሰማቸውን ጥልቅ ሀዘን እና የልብ ስብራት አጋርተዋል።
22 hours ago
የCPJ የ2026 ዓለም አቀፍ የፕሬስ ነፃነት ሽልማት አሸናፊዎች ተገለጹ
#ethiopia | የጋዜጠኞችን ጥበቃ ኮሚቴ (CPJ) ለ36ኛ ጊዜ የሚያዘጋጀውን ዓመታዊ International Press Freedom Awards (IPFA) የ2026 ተሸላሚ ጋዜጠኞችን ይፋ አድርጓል።
የሽልማት ሥነ ሥርዓቱ ኅዳር 19 ቀን 2026 በኒውዮርክ ከተማ የሚካሄድ ሲሆን፣ ከተለያዩ አገራት የተውጣጡ ጋዜጠኞች በድፍረታቸውና በሙያዊ ተግባራቸው ይሸለማሉ።
በዚህ ዓመት ከተሸለሙት መካከል ከሊባኖስ፣ ከኤርትራ፣ ከሀንጋሪ፣ ከኮሎምቢያ እና ከሚያንማር የመጡ ጋዜጠኞች ይገኛሉ።
ክርስቲና አሲ – ሊባኖስ
የAFP ፎቶ ጋዜጠኛ ክርስቲና አሲ በጥቅምት 2023 በእስራኤል–ሊባኖስ ድንበር ዘገባ ስትሰራ በደረሰባት ጥቃት ቀኝ እግሯን አጥታለች፤ የሮይተርስ ጋዜጠኛ ኢሳም አብዳላህም በዚያው ጥቃት ተገድሏል።
CPJ እንደሚለው፣ በዚህ ጉዳይ እስካሁን ተጠያቂ የሆነ አካል የለም። አሲ ከዚያ በኋላ ለጋዜጠኞች ደኅንነትና ለፍትሕ ድምፅ ሆና እየሠራች ነው።
"ኤርትራ 16"
CPJ በዚህ ዓመት ለ25 ዓመታት ያለ ፍርድ ታስረው የቆዩትን "ኤርትራ 16" የተባሉ 16 ጋዜጠኞች በጋራ ሸልሟል።
እነዚህ ጋዜጠኞች በ2001 የግል ሚዲያዎች ከተዘጉ በኋላ ታስረው ሲሆን፣ እስካሁን ክስ አልቀረበባቸውም፣ ፍርድ ቤትም አልቀረቡም። የጤናቸውና የሕይወታቸው ሁኔታ እንኳን በግልፅ አይታወቅም።
ሳቦልች ፓንዪ – ሀንጋሪ
የምርመራ ጋዜጠኛው ሳቦልች ፓንዪ የሩሲያ ተፅዕኖ፣ ሙስናና የፖለቲካ ሥልጣን ላይ በሠራቸው ዘገባዎች የሚታወቅ ሲሆን፣ በ2026 የሀንጋሪ ምርጫ ዋዜማ ከባድ ጫናና የስለላ ክስ ተጋፍጦበታል።
ኤስቴፋኒ ሮድሪጌዝ – ኮሎምቢያ
በአሜሪካ የስፓኒሽ ቋንቋ ሚዲያ Nashville Noticias ዘጋቢ የሆነችው ኤስቴፋኒ ሮድሪጌዝ በ2026 በICE ተይዛ ታስራ ነበር።
CPJ ጉዳዩ በስደተኞች ጉዳይ ላይ በምታደርገው ዘገባ ምክንያት በጋዜጠኞች ላይ የሚደረግ ጫናን የሚያሳይ ነው ብሏል።
ሳይ ዛው ታይክ – ሚያንማር
የMyanmar Now ፎቶ ጋዜጠኛ ሳይ ዛው ታይክ በ2023 የCyclone Mocha ጉዳትን ሲዘግብ ተይዞ 20 ዓመት ከባድ እስራት ተፈርዶበታል።
CPJ እንደሚለው ሚያንማር በዓለም ላይ ጋዜጠኞችን በእስር ከሚያቆዩ አገራት መካከል ሁለተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች።
የGwen Ifill የፕሬስ ነፃነት ሽልማት
የ2026 Gwen Ifill Press Freedom Award የኤል ሳልቫዶር ጋዜጠኛና El Faro መስራች ካርሎስ ዳዳ ተሸላሚ ሆኗል።
ዳዳ ለዓመታት በሙስና፣ በወንጀለኛ ቡድኖች፣ በሰብዓዊ መብቶች ጥሰትና በመንግሥት አሰራር ላይ የምርመራ ዘገባዎችን በማቅረብ የሚታወቅ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት ከመንግሥታዊ ጫና የተነሳ በስደት እየኖረ ነው።
CPJ እንደገለጸው፣ የ2026 ተሸላሚዎች የተመረጡት ከፍተኛ አደጋና ጫና ውስጥ ሆነው ለሕዝብ እውነታን ለማድረስ ባሳዩት ድፍረትና ቁርጠኝነት መሠረት ነው።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#ethiopia | የጋዜጠኞችን ጥበቃ ኮሚቴ (CPJ) ለ36ኛ ጊዜ የሚያዘጋጀውን ዓመታዊ International Press Freedom Awards (IPFA) የ2026 ተሸላሚ ጋዜጠኞችን ይፋ አድርጓል።
የሽልማት ሥነ ሥርዓቱ ኅዳር 19 ቀን 2026 በኒውዮርክ ከተማ የሚካሄድ ሲሆን፣ ከተለያዩ አገራት የተውጣጡ ጋዜጠኞች በድፍረታቸውና በሙያዊ ተግባራቸው ይሸለማሉ።
በዚህ ዓመት ከተሸለሙት መካከል ከሊባኖስ፣ ከኤርትራ፣ ከሀንጋሪ፣ ከኮሎምቢያ እና ከሚያንማር የመጡ ጋዜጠኞች ይገኛሉ።
ክርስቲና አሲ – ሊባኖስ
የAFP ፎቶ ጋዜጠኛ ክርስቲና አሲ በጥቅምት 2023 በእስራኤል–ሊባኖስ ድንበር ዘገባ ስትሰራ በደረሰባት ጥቃት ቀኝ እግሯን አጥታለች፤ የሮይተርስ ጋዜጠኛ ኢሳም አብዳላህም በዚያው ጥቃት ተገድሏል።
CPJ እንደሚለው፣ በዚህ ጉዳይ እስካሁን ተጠያቂ የሆነ አካል የለም። አሲ ከዚያ በኋላ ለጋዜጠኞች ደኅንነትና ለፍትሕ ድምፅ ሆና እየሠራች ነው።
"ኤርትራ 16"
CPJ በዚህ ዓመት ለ25 ዓመታት ያለ ፍርድ ታስረው የቆዩትን "ኤርትራ 16" የተባሉ 16 ጋዜጠኞች በጋራ ሸልሟል።
እነዚህ ጋዜጠኞች በ2001 የግል ሚዲያዎች ከተዘጉ በኋላ ታስረው ሲሆን፣ እስካሁን ክስ አልቀረበባቸውም፣ ፍርድ ቤትም አልቀረቡም። የጤናቸውና የሕይወታቸው ሁኔታ እንኳን በግልፅ አይታወቅም።
ሳቦልች ፓንዪ – ሀንጋሪ
የምርመራ ጋዜጠኛው ሳቦልች ፓንዪ የሩሲያ ተፅዕኖ፣ ሙስናና የፖለቲካ ሥልጣን ላይ በሠራቸው ዘገባዎች የሚታወቅ ሲሆን፣ በ2026 የሀንጋሪ ምርጫ ዋዜማ ከባድ ጫናና የስለላ ክስ ተጋፍጦበታል።
ኤስቴፋኒ ሮድሪጌዝ – ኮሎምቢያ
በአሜሪካ የስፓኒሽ ቋንቋ ሚዲያ Nashville Noticias ዘጋቢ የሆነችው ኤስቴፋኒ ሮድሪጌዝ በ2026 በICE ተይዛ ታስራ ነበር።
CPJ ጉዳዩ በስደተኞች ጉዳይ ላይ በምታደርገው ዘገባ ምክንያት በጋዜጠኞች ላይ የሚደረግ ጫናን የሚያሳይ ነው ብሏል።
ሳይ ዛው ታይክ – ሚያንማር
የMyanmar Now ፎቶ ጋዜጠኛ ሳይ ዛው ታይክ በ2023 የCyclone Mocha ጉዳትን ሲዘግብ ተይዞ 20 ዓመት ከባድ እስራት ተፈርዶበታል።
CPJ እንደሚለው ሚያንማር በዓለም ላይ ጋዜጠኞችን በእስር ከሚያቆዩ አገራት መካከል ሁለተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች።
የGwen Ifill የፕሬስ ነፃነት ሽልማት
የ2026 Gwen Ifill Press Freedom Award የኤል ሳልቫዶር ጋዜጠኛና El Faro መስራች ካርሎስ ዳዳ ተሸላሚ ሆኗል።
ዳዳ ለዓመታት በሙስና፣ በወንጀለኛ ቡድኖች፣ በሰብዓዊ መብቶች ጥሰትና በመንግሥት አሰራር ላይ የምርመራ ዘገባዎችን በማቅረብ የሚታወቅ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት ከመንግሥታዊ ጫና የተነሳ በስደት እየኖረ ነው።
CPJ እንደገለጸው፣ የ2026 ተሸላሚዎች የተመረጡት ከፍተኛ አደጋና ጫና ውስጥ ሆነው ለሕዝብ እውነታን ለማድረስ ባሳዩት ድፍረትና ቁርጠኝነት መሠረት ነው።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
Sponsored by
Surafel
24 hours ago
የኤቦላ ቫይረስ በአሳሳቢ ሁኔታ እየተሰራጨ ነው ሲል ድንበር የለሽ የሐኪሞች ቡድን አሳወቀ
የዛሬ ሁለት ወራት ተኩል ገደማ በኮንጎ የተከሰተው የኤቦላ ቫይረስ ወረርሽኝ በአሳሳቢና ባልተጠበቀ ሁኔታ በሀገሪቱ እየተሰራጨ ነው ሲል ድንበር የለሽ የሐኪሞች ቡድን በምህፃሩ MSF አስታወቀ።
ድርጅቱ እንደሚለው በሽታውን ለመከላከል የህክምና ባለሞያዎች ያላሰለሰ ጥረት እያደረጉ ቢሆንም፤ ወረርሽኙ ከመቼውም ጊዜ በበለጠ በአሳሳቢ ሁኔታ እየተሰራጨ ይገኛል።
እስካሁን ከ3 ሺህ 600 በላይ ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው በላቦራቶሪ ተረጋገጧል፤ ቁጥራቸው 1 ሺህ 500 የሚጠጋ ሰዎችም ሞተዋል።
በአሁኑ ጊዜ ዋናው ተግዳሮት ባለሥልጣናት በበሽታው ከተያዙ ሰዎች ጋር ግንኙነት ያላቸውን ሰዎች መለየት እንደተሳናቸው መሆኑ ነው።
ቡንያ በተባለው አካባቢ የሚገኝ የህክምና ማዕከል ውስጥ ከሚገኙት በሽተኞች ውስጥ 90 በመቶው ከዚህ ቀደም በኤቦላ ቫይረስ ከተያዙ ሰዎች ጋር ንክኪ እንዳላቸው የሚታወቅ ነገር የለም።
የዓለም የጤና ድርጅት ዋና ኃላፊ ዶክተር ቴዎድሮስ አድሃኖም ከመንግሥት ኃላፊዎችና ከሰብአዊ ድርጅቶች ጋር ለመነጋገር ዛሬ ወደ ኮንጎ ኪንሻሳ ሄደዋል።
ዶክተር ቴዎድሮስ የኤቦላ ወረርሽኝ ከተሰከሰተ ወዲህ ወደ ኮንጎ ሲጓዙ የዛሬው ለሁለተኛ ጊዜ ነው።
Seledadotio
Seledadotio
የዛሬ ሁለት ወራት ተኩል ገደማ በኮንጎ የተከሰተው የኤቦላ ቫይረስ ወረርሽኝ በአሳሳቢና ባልተጠበቀ ሁኔታ በሀገሪቱ እየተሰራጨ ነው ሲል ድንበር የለሽ የሐኪሞች ቡድን በምህፃሩ MSF አስታወቀ።
ድርጅቱ እንደሚለው በሽታውን ለመከላከል የህክምና ባለሞያዎች ያላሰለሰ ጥረት እያደረጉ ቢሆንም፤ ወረርሽኙ ከመቼውም ጊዜ በበለጠ በአሳሳቢ ሁኔታ እየተሰራጨ ይገኛል።
እስካሁን ከ3 ሺህ 600 በላይ ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው በላቦራቶሪ ተረጋገጧል፤ ቁጥራቸው 1 ሺህ 500 የሚጠጋ ሰዎችም ሞተዋል።
በአሁኑ ጊዜ ዋናው ተግዳሮት ባለሥልጣናት በበሽታው ከተያዙ ሰዎች ጋር ግንኙነት ያላቸውን ሰዎች መለየት እንደተሳናቸው መሆኑ ነው።
ቡንያ በተባለው አካባቢ የሚገኝ የህክምና ማዕከል ውስጥ ከሚገኙት በሽተኞች ውስጥ 90 በመቶው ከዚህ ቀደም በኤቦላ ቫይረስ ከተያዙ ሰዎች ጋር ንክኪ እንዳላቸው የሚታወቅ ነገር የለም።
የዓለም የጤና ድርጅት ዋና ኃላፊ ዶክተር ቴዎድሮስ አድሃኖም ከመንግሥት ኃላፊዎችና ከሰብአዊ ድርጅቶች ጋር ለመነጋገር ዛሬ ወደ ኮንጎ ኪንሻሳ ሄደዋል።
ዶክተር ቴዎድሮስ የኤቦላ ወረርሽኝ ከተሰከሰተ ወዲህ ወደ ኮንጎ ሲጓዙ የዛሬው ለሁለተኛ ጊዜ ነው።
Seledadotio
Seledadotio
1 day ago
የቀድሞው የኢትዮጵያ አየር መንገድ መሪ ተወልደ ገብረማሪያም የኤር ኢንዲያ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሆነው ተሾሙ
የሕንድ ሁለተኛው ትልቁ አየር መንገድ የቀድሞውን የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ሥራ አስፈፋሚ ተወልደ ወልደማሪያምን ዋና ሥራ አስፈጻሚው አድርጎ መሾሙን አስታወቀ።
የኢትዮጵያ አየር መንገድን ከአስር ዓመት በላይ የመሩት እና አየር መንገዱን ከአፍሪካ ግዙፉ እንዲሁም ቀዳሚው በማድረግ አሁን ከደረሰበት ደረጃ ላይ በማድረስ ቁልፍ ሚና የነበራቸው ተወልደ፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ያካሄደውን የባለ ብዙ ሚሊዮን ዶላር ማስፋፋት እና ባለ ብዙ አውሮፕላኖች ባለቤት እንዲሆን ያስቻሉ መሆናቸው ይነገራል።
አቶ ተወልደ ገብረማሪያም በኢትዮጵያ አየር መንገድ ስኬት ላይ ብቻ ሳይሆን ፈተናዎች በገጠሙት ጊዜ ተቋሙ ተግዳሮቶችን ተቋቁሞ በስኬት እንዲያልፍ አድርገዋል።
በተለይም በአየር መንገዱ ታሪክ ውስጥ ከባድ በነበሩት የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ወቅት በርካታ አየር መንገዶች ለኪሳራ እና ከሥራ ውጪ ለመሆን ሲገደዱ የኢትዮጵያ አየር መንገድ በሥራው ላይ ለውጥ በማድረግ ትርፋማ ለመሆን አስችለውታል።
በተጨማሪም ከአዲስ አበባ ወደ ናይሮቢ ሲበር ተከስክሶ ሁሉም መንገደኞች እና የአውሮፕላኑ ሠራተኞች ከሞቱበት የቦይን 737 ማክስ አውሮፕላን አደጋ ወቅት የአየር መንገዱን ጥንካሬ ዝና ጠብቀው ከቀውሱ ለመውጣት መቻላቸው ከሚጠቀሱላችው ስኬቶቻቸው መካከል ናቸው።
አቶ ተወልደ ገብረማሪያም አሁን የዋና ሥራ አስፈጻሚውን ቦታ የሚረከቡት ኤር ኢንዲያ አየር መንገድ ባለፈው የአውሮፓውያን ዓመት አውሮፕላኑ ተከስክሶ 260 መንገደኞች ከሞቱ በኋላ በከባድ ፈተና ውስጥ ይገኛል።
አየር መንገዱ በተጨማሪም ከፍተኛ የገንዘብ እና የሥራውን የማካሄድ ፈተና የገጠመው ሲሆን፣ ከደረሰበት አደጋ ተያይዞ በአቪየሽን ተቆጣጣሪ አካላት ጥብቅ ቁጥጥር የሚደረግበት ነው።
አቶ ተወልደ የመሪነት ኃላፊነቱን የሚረከቡት ኤር ኢንዲያ በሚያጓጉዛቸው መንገደኞች ብዛት በሕንድ ውስጥ ካሉ አየር መንገዶች ሁለተኛው ትልቁ አየር መንገድ ነው።
ታታ ግሩፕ 75 በመቶ የባለቤትንት ድርሻውን እንዲሁም የሴንጋፖር አየር መንገድ 25 ባለቤትነት ያለው ወደ 200 የሚጠጉ አውሮፕላኖች እና ከ31 ሺህ በላይ ሠራተኞች የሚሰስተደድረው አየር መንገዱ ወደ 90 ዓለም አቀፍ እና የአገር ውስጥ የበረራ መስመሮች አሉት።
በኢትዮጵያ አየር መንገድ ውስጥ ከ20 ዓመታት በላይ በተለያዩ ኃላፊነቶች ላይ የሠሩት አቶ ተወልደ ገብረማሪያም የአየር መንገዱ ዋና ሥራ አስፈጻሚ የሆኑት በጥር 2003 ዓ.ም. ነበረ።
አቶ ተወልደ በተባበሩት መንግሥታት ውስጥ ዘላቂነት ባለው ትራንስፖርት ዘርፍ ከፍተኛ የአማካሪዎች ቡድን አባል ሆነው ሠርተዋል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ አባል በሆነበት የስታር አሊያንስ ዋና የቦርድ አባል፣ የዓለም አቀፉ የትራንስፖርት ማኅበር (አይኤቲኤ) የቦርድ አባል በተጨማሪም የአፍሪካ የአየር መንገዶች ማኅበር (ኤኤፍአርኤኤ) የዋና ኮሚቴ አባል በመሆን አገልግለዋል።
አቶ ተወልደ የአፍሪካ የጉዞ ማኅበር (ኤቲኤ) የቦርድ አባል እና የኢትዮጵያ የቱሪዝም ድርጅት (ኢቲኦ) የዳይሬክተሮች ቦርድ አባልም ነበሩ።
አቶ ተወልደ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሆነው ባገለገሉባቸው በርካታ ዓመታት የተለያዩ ሽልማቶችን አግኝተዋል።
ከሽልማቶቹ መካከል የዓመቱ የአፍሪካ ምርጥ ዋና ሥራ አስፈጻሚ፣ ምርጥ የአፍሪካ የቢዝነስ መሪ፣ የቀጣናዊ የአየር መንገድ አመራር ሽልማት እንዲሁም ምርጥ ፆታን ያማከለ ሥራ አስፈፃሚ የሚሉት ይጠቀሳሉ።
የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ በኢኮኖሚክስ፣ ሁለተኛ ዲግሪያቸውን ከዩናይትድ ኪንግደም ኦፕን ዩኒቨርስቲ በንግድ አስተዳደር ያገኙ ሲሆን ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የክብር ዶክትሬትም ተበርክቶላቸዋል።
አቶ ተወልደ ገብረ ማሪያም ከአስር ዓመት በላይ በስኬት የመሩትን የኢትዮጵያ አየር መንገድን የለቀቁት በጤና ሁኔታን በምክንያት ጠቅሰው በ2014 ዓ.ም. ነበር።
BBC
የሕንድ ሁለተኛው ትልቁ አየር መንገድ የቀድሞውን የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ሥራ አስፈፋሚ ተወልደ ወልደማሪያምን ዋና ሥራ አስፈጻሚው አድርጎ መሾሙን አስታወቀ።
የኢትዮጵያ አየር መንገድን ከአስር ዓመት በላይ የመሩት እና አየር መንገዱን ከአፍሪካ ግዙፉ እንዲሁም ቀዳሚው በማድረግ አሁን ከደረሰበት ደረጃ ላይ በማድረስ ቁልፍ ሚና የነበራቸው ተወልደ፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ያካሄደውን የባለ ብዙ ሚሊዮን ዶላር ማስፋፋት እና ባለ ብዙ አውሮፕላኖች ባለቤት እንዲሆን ያስቻሉ መሆናቸው ይነገራል።
አቶ ተወልደ ገብረማሪያም በኢትዮጵያ አየር መንገድ ስኬት ላይ ብቻ ሳይሆን ፈተናዎች በገጠሙት ጊዜ ተቋሙ ተግዳሮቶችን ተቋቁሞ በስኬት እንዲያልፍ አድርገዋል።
በተለይም በአየር መንገዱ ታሪክ ውስጥ ከባድ በነበሩት የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ወቅት በርካታ አየር መንገዶች ለኪሳራ እና ከሥራ ውጪ ለመሆን ሲገደዱ የኢትዮጵያ አየር መንገድ በሥራው ላይ ለውጥ በማድረግ ትርፋማ ለመሆን አስችለውታል።
በተጨማሪም ከአዲስ አበባ ወደ ናይሮቢ ሲበር ተከስክሶ ሁሉም መንገደኞች እና የአውሮፕላኑ ሠራተኞች ከሞቱበት የቦይን 737 ማክስ አውሮፕላን አደጋ ወቅት የአየር መንገዱን ጥንካሬ ዝና ጠብቀው ከቀውሱ ለመውጣት መቻላቸው ከሚጠቀሱላችው ስኬቶቻቸው መካከል ናቸው።
አቶ ተወልደ ገብረማሪያም አሁን የዋና ሥራ አስፈጻሚውን ቦታ የሚረከቡት ኤር ኢንዲያ አየር መንገድ ባለፈው የአውሮፓውያን ዓመት አውሮፕላኑ ተከስክሶ 260 መንገደኞች ከሞቱ በኋላ በከባድ ፈተና ውስጥ ይገኛል።
አየር መንገዱ በተጨማሪም ከፍተኛ የገንዘብ እና የሥራውን የማካሄድ ፈተና የገጠመው ሲሆን፣ ከደረሰበት አደጋ ተያይዞ በአቪየሽን ተቆጣጣሪ አካላት ጥብቅ ቁጥጥር የሚደረግበት ነው።
አቶ ተወልደ የመሪነት ኃላፊነቱን የሚረከቡት ኤር ኢንዲያ በሚያጓጉዛቸው መንገደኞች ብዛት በሕንድ ውስጥ ካሉ አየር መንገዶች ሁለተኛው ትልቁ አየር መንገድ ነው።
ታታ ግሩፕ 75 በመቶ የባለቤትንት ድርሻውን እንዲሁም የሴንጋፖር አየር መንገድ 25 ባለቤትነት ያለው ወደ 200 የሚጠጉ አውሮፕላኖች እና ከ31 ሺህ በላይ ሠራተኞች የሚሰስተደድረው አየር መንገዱ ወደ 90 ዓለም አቀፍ እና የአገር ውስጥ የበረራ መስመሮች አሉት።
በኢትዮጵያ አየር መንገድ ውስጥ ከ20 ዓመታት በላይ በተለያዩ ኃላፊነቶች ላይ የሠሩት አቶ ተወልደ ገብረማሪያም የአየር መንገዱ ዋና ሥራ አስፈጻሚ የሆኑት በጥር 2003 ዓ.ም. ነበረ።
አቶ ተወልደ በተባበሩት መንግሥታት ውስጥ ዘላቂነት ባለው ትራንስፖርት ዘርፍ ከፍተኛ የአማካሪዎች ቡድን አባል ሆነው ሠርተዋል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ አባል በሆነበት የስታር አሊያንስ ዋና የቦርድ አባል፣ የዓለም አቀፉ የትራንስፖርት ማኅበር (አይኤቲኤ) የቦርድ አባል በተጨማሪም የአፍሪካ የአየር መንገዶች ማኅበር (ኤኤፍአርኤኤ) የዋና ኮሚቴ አባል በመሆን አገልግለዋል።
አቶ ተወልደ የአፍሪካ የጉዞ ማኅበር (ኤቲኤ) የቦርድ አባል እና የኢትዮጵያ የቱሪዝም ድርጅት (ኢቲኦ) የዳይሬክተሮች ቦርድ አባልም ነበሩ።
አቶ ተወልደ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሆነው ባገለገሉባቸው በርካታ ዓመታት የተለያዩ ሽልማቶችን አግኝተዋል።
ከሽልማቶቹ መካከል የዓመቱ የአፍሪካ ምርጥ ዋና ሥራ አስፈጻሚ፣ ምርጥ የአፍሪካ የቢዝነስ መሪ፣ የቀጣናዊ የአየር መንገድ አመራር ሽልማት እንዲሁም ምርጥ ፆታን ያማከለ ሥራ አስፈፃሚ የሚሉት ይጠቀሳሉ።
የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ በኢኮኖሚክስ፣ ሁለተኛ ዲግሪያቸውን ከዩናይትድ ኪንግደም ኦፕን ዩኒቨርስቲ በንግድ አስተዳደር ያገኙ ሲሆን ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የክብር ዶክትሬትም ተበርክቶላቸዋል።
አቶ ተወልደ ገብረ ማሪያም ከአስር ዓመት በላይ በስኬት የመሩትን የኢትዮጵያ አየር መንገድን የለቀቁት በጤና ሁኔታን በምክንያት ጠቅሰው በ2014 ዓ.ም. ነበር።
BBC
1 day ago
በትግራይ «70 ካሬ» የተፈናቃዮች ማዕከል በጣለው ከባድ ዝናብ እና ንፋስ ከ20 በላይ ጊዜያዊ መጠለያዎች ሙሉ በሙሉ ወደሙ፡፡
የምዕራብ ትግራይ ሲቪል ማህበረሰብ ድርጅት (ፅላል) አስተባባሪ አቶ ዘበኖም ኪዱ ለትግራይ ቲቪ እንደገለጹት፤ ትላንት በጣለው ከባድ ዝናብ እና ንፋስ መጠለያዎቹ ከጥቅም ውጪ ከመሆናቸውም በላይ በንብረት ላይ ከፍተኛ ኪሳራ ደርሷል።
በተጨማሪም አደጋው በሰዎች ላይ አካላዊ ጉዳት ያደረሰ ሲሆን፣ በተለይም አረጋውያን ላይ ጉዳት በመድረሱ ለሕክምና እርዳታ ወደ ጤና ተቋም መወሰዳቸውን አስተባባሪው ጨምረው ገልጸዋል።
በደረሰው አደጋ ምክንያት ተፈናቃዮቹ ለበለጠ እንግልት እና ችግር መጋለጣቸውን የጠቆሙት አቶ ዘበኖም፣ የሰብአዊነት ስሜት ያለው አካል ሁሉ አስቸኳይ ድጋፍ እንዲያደርግ ጥሪ አቅርበዋል።
የተፈናቀለው ሕዝብ በከባድ ችግር ውስጥ እንደሚገኝ ያመለከተው የምዕራብ ትግራይ ሲቪል ማህበረሰብ ድርጅት፣ ለችግሩ ዘላቂ መፍትሔ የሚሆነው ተፈናቃዮች ወደ ቀደመ መኖሪያቸው የሚመለሱበት ሁኔታ ሲመቻች ብቻ እንደሆነ አጽንኦት ሰጥቷል ሲል ዘገባው መልክቷል።
Seledadotio
Seledadotio
የምዕራብ ትግራይ ሲቪል ማህበረሰብ ድርጅት (ፅላል) አስተባባሪ አቶ ዘበኖም ኪዱ ለትግራይ ቲቪ እንደገለጹት፤ ትላንት በጣለው ከባድ ዝናብ እና ንፋስ መጠለያዎቹ ከጥቅም ውጪ ከመሆናቸውም በላይ በንብረት ላይ ከፍተኛ ኪሳራ ደርሷል።
በተጨማሪም አደጋው በሰዎች ላይ አካላዊ ጉዳት ያደረሰ ሲሆን፣ በተለይም አረጋውያን ላይ ጉዳት በመድረሱ ለሕክምና እርዳታ ወደ ጤና ተቋም መወሰዳቸውን አስተባባሪው ጨምረው ገልጸዋል።
በደረሰው አደጋ ምክንያት ተፈናቃዮቹ ለበለጠ እንግልት እና ችግር መጋለጣቸውን የጠቆሙት አቶ ዘበኖም፣ የሰብአዊነት ስሜት ያለው አካል ሁሉ አስቸኳይ ድጋፍ እንዲያደርግ ጥሪ አቅርበዋል።
የተፈናቀለው ሕዝብ በከባድ ችግር ውስጥ እንደሚገኝ ያመለከተው የምዕራብ ትግራይ ሲቪል ማህበረሰብ ድርጅት፣ ለችግሩ ዘላቂ መፍትሔ የሚሆነው ተፈናቃዮች ወደ ቀደመ መኖሪያቸው የሚመለሱበት ሁኔታ ሲመቻች ብቻ እንደሆነ አጽንኦት ሰጥቷል ሲል ዘገባው መልክቷል።
Seledadotio
Seledadotio
1 day ago
በፋብሪካ የሚመረቱ አልኮሎችና ትንባሆ ላይ የኤክሳይዝ ታክስ መጣል የምርቶቹን ዋጋ አንዲጨምር በማድረጉ የምርቶቹ የተጠቃሚዎች ቁጥር መቀነሱን ጥናት አሳየ፡፡
በሌላ በኩል ግን ጠጅ ፣ ጠላ ፣ አረቄ የመሳሰሉት ምርቶች ተጠቃሚያቸው መብዛቱን በጥናቱ ግኝት ተጠቅሷል፡፡
ጥናቱን ያጠናው በጤናው መስክ ጥናትና ምርምሮችን የሚያካሂደው ፍኖት የተሰኘ ድርጅት ነው ።
ድርጅቱ ይህን ጥናት ይፋ ያደረገው ከስድስት ዓመት በፊት በአልኮል እና በትንባሆ ላይ የተጣለው ኤክሳይዝ ታክስ ምን ውጤት እንዳመጣ በአማራ፣ኦሮሚያና በአዲስ አበባ ላይ ያካሄደው ዳሰሳዊ ጥናት ነው ።
በአልኮልና በትንባሆ ምርቶች ላይ የተጣለው ኤክሳይዝ ታክስ የተጠቃሚዎችን ቁጥር ከ10 እስከ 20 በመቶ እንዲቀንስ አድርጓል ሲሉ በፍኖት አሶሼት የሄልዝ ኬር ፋይናንሲንግ ባለሙያና አማካሪ የሆኑት ፕሮፌሰር አስማማው አጥናፉ የጥናቱን ውጤት ጠቅሰው ነግረውናል፡፡
በሌላ በኩል መንግስት የሚያገኘው ገቢ እንዲያድግ ማስቻሉንም በጥናቱ አረጋግጠናል ይላሉ።
የፍኖት አሶሼት መስራች አባል እና የፍኖት ፕሮጀክት ዳይሬክተር ዶ/ር ፅኑኤል ግርማ በበኩላቸው
እንደ ትንባሆ እና ሲጋራ ምርቶች በህገወጥ መንገድ አሁንም እየገቡ መሆኑን ነግረውናል።
በፍኖት አሶሼት የፋይናንሲንግ ም/ ዳይሬክተር ዶ/ር ግርማ ደዬ በፋብሪካዎች የማይመረቱ፣ የአልኮል መጠናቸውም በማይታወቁ እንደ ጠላ፣ ጠጅ እና አረቄ ያሉ መጠጦች በሰዎች ጤና ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ እያመጡ ነው ብለዋል ።
በሌላ በኩል በህገወጥ የሚገቡ ምርቶችን መቆጣጠር እንደሚገባም ጠቁመዋል ።
Via Sheger Fm
በሌላ በኩል ግን ጠጅ ፣ ጠላ ፣ አረቄ የመሳሰሉት ምርቶች ተጠቃሚያቸው መብዛቱን በጥናቱ ግኝት ተጠቅሷል፡፡
ጥናቱን ያጠናው በጤናው መስክ ጥናትና ምርምሮችን የሚያካሂደው ፍኖት የተሰኘ ድርጅት ነው ።
ድርጅቱ ይህን ጥናት ይፋ ያደረገው ከስድስት ዓመት በፊት በአልኮል እና በትንባሆ ላይ የተጣለው ኤክሳይዝ ታክስ ምን ውጤት እንዳመጣ በአማራ፣ኦሮሚያና በአዲስ አበባ ላይ ያካሄደው ዳሰሳዊ ጥናት ነው ።
በአልኮልና በትንባሆ ምርቶች ላይ የተጣለው ኤክሳይዝ ታክስ የተጠቃሚዎችን ቁጥር ከ10 እስከ 20 በመቶ እንዲቀንስ አድርጓል ሲሉ በፍኖት አሶሼት የሄልዝ ኬር ፋይናንሲንግ ባለሙያና አማካሪ የሆኑት ፕሮፌሰር አስማማው አጥናፉ የጥናቱን ውጤት ጠቅሰው ነግረውናል፡፡
በሌላ በኩል መንግስት የሚያገኘው ገቢ እንዲያድግ ማስቻሉንም በጥናቱ አረጋግጠናል ይላሉ።
የፍኖት አሶሼት መስራች አባል እና የፍኖት ፕሮጀክት ዳይሬክተር ዶ/ር ፅኑኤል ግርማ በበኩላቸው
እንደ ትንባሆ እና ሲጋራ ምርቶች በህገወጥ መንገድ አሁንም እየገቡ መሆኑን ነግረውናል።
በፍኖት አሶሼት የፋይናንሲንግ ም/ ዳይሬክተር ዶ/ር ግርማ ደዬ በፋብሪካዎች የማይመረቱ፣ የአልኮል መጠናቸውም በማይታወቁ እንደ ጠላ፣ ጠጅ እና አረቄ ያሉ መጠጦች በሰዎች ጤና ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ እያመጡ ነው ብለዋል ።
በሌላ በኩል በህገወጥ የሚገቡ ምርቶችን መቆጣጠር እንደሚገባም ጠቁመዋል ።
Via Sheger Fm
1 day ago
መዝሙረ ሄላም ላይ የተደረገ አጭር ኂሳዊ ንባብ
ከቢኒያም አቡራ
#ethiopia | አዳም ረታ ታሪክን ከነገሥታት፣ ከመሪዎች፣ ማኅበረሰቡ ባበጀው ድልድል ውስጥ ‹ላዕላይ› ከሚባሉት ደረጃዎች አንጻር አያስመለክተንም። ታሪካዊ ከሚባሉ አጋጣሚዎች ውስጥ የተዘነጉትን ጥቃቅን የታሪክ ኹነተ-ደቂቅ (micro-events) ይመርጣል። ይወስዳል መንገድ ላይ … “ቀዳዳ” በተሰኘው ታሪክ ላይ ፍንዳታውን ከሚሞት ዘመድ፣ ከሚደነግጥ ለማኝ፣ ከሚሰነጠቅ የወፍ እንቁላል፣ ከሚፈስ የእናት ወተት ጋር Micro-Macro Connection በመፍጠር የትልቁ ቀዳዳ መፈጠርን ከሚጢጢዬ ሽንቁሮች ጋር ያስተሳስርልናል። እንዲህ ያሉ የኒው ሂስቶሪሲዝም ባሕሪያትን ከዚህ ቀደም ባሳተማቸው መጻሕፍቱ ውስጥ በተለያየ መጠን እናገኛለን።
Adam Reta አዳም ረታ "መዝሙረ ሄላም" በተሰኘው በዐዲሱ መጽሐፉ ላይም በኢትዮጵያ ታሪካዊ-ፖለቲካዊ አጋጣሚ ውስጥ እንደ ዐውራ የሚታዩትን የእድገት በኅብረት ዘመቻን እንደነ-አሮን፣ እንደነቃል … ባሉ ገጸባሕርያት በኩል፣ የሰባ ሰባቱን ድርቅ በሄላም ጡት በኩል፣ “ጥላሁን ለምን ለምን ሞተ” እየተባለ ኢዮቤልዩ ቤተመንግሥት ጋር የተደረገውን ሰላማዊ ሰልፍ በሡልጣን በኩል፣ የከተማ መሬት ዐዋጅን በተለያዩ ግለሰቦች በኩል … እናያለን። በዚህም የታሪክን ትልቅ ካርታ ለመረዳት የተረሱና የጠለሉ ታሪኮችን ይመረምራል። ስለዚህ ነቁጣዊ ማኅበራዊ ክስተቶችን ወደ ታሪክ ምኩራብ በማምጣት ከትልቁ የታሪክ ምሥል ጎን ያስተያያል። ይህ ደግሞ የኒው ሂስቶሪሲዝም ኹነኛ ማጠንጠኛ ነው።
ልክ “ይወስዳል መንገድ ያመጣል መንገድ …” በተሰኘው መጽሐፉ ውስጥ ባለው “የመንግሥቱ ጊዜ” በሚለው ድርሰት ውስጥ፣ ትልቁን “የታኅሣሥ ግርግር”ን እንደ መቼት አምጥቶ የተጻፈውና የተተኮረው ግን ኹነተ-ደቂቅ (micro-events) ላይ ነው። ስለግርማሜ ንዋይ፣ ስለኮሌኔል ወርቅነህ ገበየሁ፣ ሰለጄነራል ሙልጌታ ቡሊ አይደለም የሚያትተው። ስለአንድ ብላቴና ከእንቅልፍ መነሳት፣ ስለገበጣ ጨዋታ፣ ቤተክርስቲያን ውስጥ ሕፃናትን አሰብስቦ ‹ኪራላይሶን› የሚያስብል ካሕን፣ ስለመንደር ውስጥ ሐሜቶች፣ ስለግለሰቦች ፍርሃት፣ በአጋጣሚ ስላየው አስደናቂ አሞራ … ያወጋል። የታሪክ አጋጣሚ አምጥቶ በታሪክ ውስጥ ግለሰቦች ላይ ስለሚረብበው የታሪክ መንፈስ ያትታል። ልክ እንደዚሁ መዝሙረ ሄላም ላይም ጽሑፉ ታሪክን አያብራራም፤ ነገር ግን ታሪክ እንዴት በሰው ልብ ውስጥ እንደሚኖር ያሳያል። በዚህ ኹነተ-ደቂቅ (micro-event) ምክንያት በዘመኑ ላይ ያገነገነውን ባሕላዊ እምነትን፣ የሥልጣን መዋቅርን፣ የወል ግንዛቤን አጨንቁረን እንድንመለከት ያስችለናል።
ከመንግሥት ሼልፍ ላይ ሳይኾን ከግለሰብ ጀርባ ላይ የተወሰደው የአዳም የአጻጻፍ መንገድ ከኒው ሂስቶሪስዝም ጽንሰ-ሐሳቦች ጋር በአንድ መም ላይ የሚሄዱ ናቸው። መዝሙረ ሄላም የተሰኘው ዐዲሱ የአዳም ረታ መጽሐፍ የኒው ሂስቶሪሲዝም ባሕርያትን ይጋራል። አንዳንድ ነገሮችን በዓይን መመልከት ባይቻልም በግብሩ (ቁስ ላይ በሚያደርገው ግፊት) ግን ይታወቃል። በመዝሙረ ሄላም መጽሐፍ ውስጥም አንዳንድ ነገሮችን በቀጥታ ማየት ባንችልም ቅሉ እነርሱን የሚያሳይልንን ነገሮች ግን እንቃኛለን። ዘማች ወጣት ተማሪዎችን እናያለን፤ መንግሥትን፣ ሕግንና ኃይልን ግን በቀጥታ አንመለከትም። የተማከለ ኃይል አናይም ግን የገጸባሕርያቱ የፍርሃት ምንጭ ከተማከለ ኃይል ጋር የተያያዘ ቀጭን መስመር መኖሩን እናያለን። መንግሥትም ቢኾን በቀጥታ አይገባም፤ ነገር ግን ፍርሃት እንደ ሥርዓት ዘዋሪ (system driver) ይኾናል። እንደ ሚሸል ፉኮ አገላለጽ ኃይል ከተማከለ ሥርዓት የሚመነጭ ሳይኾን በየትኛውም ቦታና ጊዜ በፍርሃት፣ በልማድ፣ በንግግር … ሊከሰት የሚችል ሂደት አይደል?
መዝሙረ ሄላም ላይ ታሪክ እንደ “circulation of social energy” ቀርቧል። መዝሙረ ሄላም ላይ መረጃ ከመንግሥት አይመጣም፤ ከግለሰብ እንጂ። የከተማ መሬት ዐዋጅም ኾነ የተማሪዎች ዘመቻ በገጸባሕርያቱ ወሬ ውስጥ ነው የሚንቀረቀበው። ይህ የመረጃ ሥርዓት ኃይል ማን እንዳለው ማን እንደሌለው ያሳያል። እንግዲህ ይህ በፉኮኛ micro-power መኾኑ ነው። በመዝሙረ ሄላም ላይ ታሪክ እንደ ወሬ እንጂ እንደ ሰነድ አይቀርብም።
ወሬ የፍርሃት ቤንዚን ነው … ፍርሃት ደግሞ በዝምታ መሸበብን ይፈጥራል … የዝምታ አፈ-ሙቅ ደግሞ ኃይለኛው እንዳይታይ ያደርጋል … የተደራጀው ኃይል ጥፋትን ሊያደርስ ባሰበ ቁጥር የወሬ ቤንዚን ይጨምራል። ሰዎች በዕቅብተ-ንግግር ራሳቸውን ሲሸብቡ ደርዝ ያለው ሙግት ይኮሰምናል፣ ንግግር ሲጠፋ ያልታወቀ አደጋ ይከሰታል፣ ፍርሃትም ይጨምራል። ያልታወቀ አደጋ ደግሞ ከታወቀ አካል ይመጣል። ስለዚህ ጥንስሱ የሚጀምረው ከወሬ እንደኾነ ያስመለክተናል። አዳም በመዝሙረ ሄላም ላይ ታሪክን እንደ “circulation of social energy” ሲያቀርብ ፕሬዝዳንት፣ ጀነራል፣ ፕሮፌሰር የኾኑ ታሪክ ከላዕላይ ያስቀመጣቸው ሰዎች አያስፈልጉትም። በአንጻሩ ሄላም ለማን እንደሳመችው ተደርጎ ብርሃኔ ያስወራው ወሬ፣ የሄላም አባት ወታደር በመኾኑ ምክንያት በካሱ፣ በሄኖክ እናት የተነዛው ወሬ እና ሄላም ከሄኖክ ጋር የተቆራረጠችበት መንገድ እንዲሁም የሄላምን የጡት ወተት በተመለከተ የተነዛው ወሬን ይጠቀማል።
መዝሙረ ሄላምን ከድኅረ-ቅኝ-አገዛዝ የኂስ መንገድ አንጻር እንመልከተው።
እውን ቅኝ-ግዛት ተረት ኾኖ ቀርቷል? በፖለቲካ፣ በኢኮኖሚ፣ በሥነልቦና ረገድ የቅኝ አገዛዝ ዳናው ሙሉ ለሙሉ ጠፍቷል? አዳም በመዝሙረ ሄላም ጽሑፍ ውስጥ ከቅኝ-ግዛት በተወረሰ መዋቅር ምክንያት የተሰናከለን ሕይወት ሊያስመለክተን ይኾን?
“ከተሞች ከቅኝ ግዛት በኋላ ሁለት ዓይነት መልክ ይኖራቸዋል፤ ለጥቂቱ የተድላ፣ ለተቀረው ደግሞ የአሳር መንደር ይኾናሉ” ይላል ፍራንዝ ፋኖን። በመዝሙረ ሄላም ላይ እና “የቢሾፍቱ ልጆች ጥላሞት” የተሰኘው ድርሰት ላይም ይህንን ነው የምንመለከተው። “ይወስዳል መንገድ ያመጣል መንገድ …” በተሰኘው መጽሐፉ ውስጥ ካሉ ጽሑፎች መካከል “የቢሾፍቱ ልጆች ጥላ ሞት” አንዱ ነው። የቢሾፍቱ ልጆች ሆቴሉን ያዩታል፤ ግን አይገቡበትም። ሆቴሉ የሀገራቸው መሬት ላይ ነው፤ እነርሱ ግን ከሆቴሉ ውጭ ናቸው። መናፈሻው ውስጥ አንዲት የፈረንጅ ልጅ ጠግባ ለልጆቹ እንደ ውሻ ዳቦ ትወረውርላቸዋለች። አፈር ላይ የወደቀን ዳቦ አራግፈው ይመገባሉ። በገዛ ሐይቃቸው ዳር ላይ ናቸው፤ ሌሎች ግን በጀልባ እየተንሸራሸሩ ይንፈላሰሳሉ። ለፈረንጆቹ ያደረው ሞገስ የላንድሮቨር ተፈናጣጭ ኾኗል። ሌሎቹ ግን ከመኪናው ውጪ ናቸው። ሞገስ እንደ እነርሱ ሕጻን ቢኾንም ለፈረንጅ በማሸርገዱ የትምህርት ቤቱ ባለቤት ሲመስል ሌሎች ልጆች ግን በገዛ መምህራቸው ይብጠለጠላሉ። የቢሾፍቱ ልጆች፣ ነጻ በተባለች ሀገር እየኖሩ በቅኝ ግዛት ጥላ ይተዳደራሉ። የቢሾፍቱ ልጆች በገዛ መንደራቸው አካሉ በማይታይ የቅኝ ግዛት እጅ ይገፋሉ። ሞገስ አይናገርም፤ የሚናገርለት አለ። ልክ የቢሾፍቱ ልጆች ላይ በአንድ ከተማ ውስጥ ሁለት የከተማ ምሥል እንደምናገኘው ሁሉ “የስንብት ቀለማት” ላይም በአዲስ አበባ ውስጥ ሁለት የከተማ ምሥል እንመለከታለን። እንደ ዘድሬክ፣ ሳተርን፣ ከተስፋዬ ወደ አሸናፊ የተቀየሩ የድሎት ምሥሎች እና የእነምትክ ጉልት፣ የእትየ እልልታ የጉርሻ መሸጫ መስኮት ያሉ የእጦት ሥዕል እናገኛለን። መዝሙረ ሄላም ላይም እንዲህ ያለ በአንድ ከተማ ላይ የሁለት ምሥሎች አደባባይ እጀግ ብዙ ቦታ ይገኛል።
በሌላኛው የድኅረ-ቅኝ-ግዛት ኂስ (postcolonial criticism) መዝሙረ ሄላምን ስንመለከት መጀመሪያ ላይ “ፈረንጅ ሲያደንቀኝና ሲገረምብኝ የሰሙ የአገሬ ደነዞች በየተራ “ካላስ የኔ ጎሳ ናት” … እያሉ መሻማት ጀመሩ ትላለች - ሄላም። በኋላ ደግሞ በተነዛባት አጓጉል ወሬ … የሄላምን ጡት ንቀው፣ አንጓጥጠው፣ አባረዋት ሲያበቁ የፈረንጅ የዱቄት ወተትን ይመርጣሉ። ይህ በባሕላዊ ማንነትና በዘመናዊነት መካከል የሚዋልል ማኅበረሰብን ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ የድኅረ-ቅኝ-ግዛት አካል ነው። በሌሎቹ የአዳም ሥራዎች ውስጥ ድኅረ-ቅኝ-ግዛት አተያይ በቋንቋና በኪነ-ጥበብ ምርጫ ውስጥ እንዴት እንደሚንፀባረቅ ያሳያል። በመዝሙረ ሄላም ላይ ደግሞ ምዕራባዊው ዓለም ለአገር በቀል መፍትኼ-ሥራይ የሚሰጠው ዋጋ ዝቅተኛ መኾኑንና የኢኮኖሚ ብዝበዛው አሁንም በረቂቅ መንገድ መቀጠሉን ያሳያል። እዚህ ላይ ሥዕለማርያም የተባለችዋን ገጸባሕርይ እና በውጭ ሀገራት የተነዙ ወሬዎችን ስንጨማምር ደግሞ የበለጠ ብዙ ለማለት ያስችላል።
መዝሙረ ሄላም ላይ እጅግ ብዙ ማኅበረሰባዊ ኂስ እናገኛለን። ለአብነት ያህል አንድ ሁለቱን እንቃኝ።
“መዝሙረ ሄላም” ላይ ማኅበረሰቡ በችላ-ባይነት አልያም በኾን ተብሎነት ልጆቹን ምን ያህል ተጠቂ እንዳደረጋቸው የሚያሳይ መልክ ተንጸባርቆበታል ማለት ይቻላል። ጋሽ ክብካብና ዘመናይ ኾን ብለው ቴዲና ሄላም ላይ የሚያደርሱትን፣ ተክለማርያም የወላጁን(የዘሪቱን) ችላ-ባይነት ለአብነት ማቅረብ ይቻላል። ማኅበረሰቡ ልጆችን “የነገ ተስፋዎች” ይላል፤ ነገር ግን ዛሬያቸው ላይ አይሠራም።
ማኅበረሰብ የመማጸኛ ከተማዎችን ወደ ተጨማሪ ግፍ መሥሪያ ቦታዎች እንደሚቀይር በአዳም መጻሕፍት ላይ በብዛት እንመለከታለን። “ይወስዳል መንገድ …” ላይ … “ቀዳዳ” በተሰኘው ታሪክ ላይ ማርታ ለደበበ በምትሰጠው ፍቅር ሳቢያ የሚሠራበትን ግፍ የምታስረሳ ብትኾንም ማኅበረሰቡ ግን ተጨማሪ ግፍ የሚሠራበት መሣሪያ ኾናለች። የስንብት ቀለማት ላይ ምኒልክ ከዚያ ሁሉ እስርና እንግልት በኋላ፣ “በፊያሜታ አርፋለሁ” ብሎ ቤቷ ሲሄድ ተጨማሪ ሕመም በጆሮው በኩል ጭንቅላቱ ላይ ይሻጥበታል። መዝሙረ ሄላም ላይም፣ ሄላም “ሙዚቃዬን ከሕዝብ ጆሮ ያደርስልኛል … ያሳርፈኛል …” ብላ የተመካችበት ምናሴ እንጦሮጦስ ይጨምራታል። ማኅበረሰባችን የመስቀል ተ ሠላጢን ግብር እንዳለው፣ ከላይ አሳልሞ ከታች በአንካሴው ጉድጓድ እንደሚምስ ያሳያል። ይህም የመልእክትን ወጭት ሰብሮ የወጣ ጥበባዊ አጻጻፍ ነው። በፈጣጣው የቀረበ የትችት ኮሶ አይደለም። ድንቅ ነው!
መዝሙረ ሄላም ላይ ከምናገኛቸው ዋና ዋና ገጸባሕርያት የተወሰኑት (አሮን፣ ቃል፣ ምናሴ፣ ሄላም) ላይ መጠነኛ ቅኝት እናድርግ።
auto-fiction ዓይነት አጻጻፍ ባለው የአሮን አተራረክ ውስጥ አሮን “system observer” መኾኑን እንገነዘባለን። ሥርዓቱን ያያል፣ ዘማቹን ያስተውላል፣ ቃለጉባኤ ይይዛል፣ ችግሩን ይመለከታል፣ ይጽፋል። አሮን የተገፋ ታሪክ ድምፅ ነው፤ ንቃት አለው፣ ግን የታሪክ ሂደትን የሚቀይር ኃይል የለውም፤ ስለዚህም ያ ሁሉ የጻፈውን ጽሑፍን ያጣል። የንቃት ችግር የለበትም፤ የማኅበራዊ ንቃት ድምፅነቱን ከዘመነ አባት ጋር ባደረገው ውይይት ውስጥ ተመልክተናል። ግን ደግሞ ይህ ብቻውን የቆመ ነጠላ ነገር ነው፤ ምክንያቱም ማኅበራዊ ተሳትፎ የለበትም። ቃል የተሰኘችው ገጸባሕርይም እንደ አሮን ናት፤ ንቃት ያላት፣ system observer ናት። ማኅበራዊ ንቃት ማኅበራዊ እንቅስቃሴ ካላገዘው ግንጥል ጌጥ ነው። ቃልና አሮን ንቃት አላቸው፤ ግን ንቃታቸውን ተግባር አላገዘውም፤ ንቃቱን የሚተገብር አደረጃጀት የላቸውም። ስለዚህ ዕጣ-ፈንታቸው ውድቀት ይኾናል። በኢትዮጵያ ውስጥ የተንሰራፋውን ይህን የድግግሞሽ አዙሪት መዝሙረ ሄላም ላይ ደራሲ አዳም ረታ በሰላ ብዕር አስቀምጧል።
የደራሲና የአርታኢ ትስስር በተንጸባረቀበት በሄላም አተራረክ ውስጥ ምናሴ የተሰኘ ገጸባሕርይ እናገኛለን። ምናሴ የ-false collective consciousness ትእምርት ነው። ምናሴዎች ለሥልጣን ይሠራሉ፣ ራሳቸውን እንደ ነጻ ያስባሉ፤ ነገር ግን የሥርዓቱ የመጠቀሚያ መሣሪያ (system functionary) ናቸው። ምናሴዎች የኦልቪቴዎች ጥይት ናቸው። ምናሴዎች የሔላምዎች ስኬት ሳይኾን የገዛ ጥቅማቸውን የሚያስቀድሙ የማኅበረሰቡ አካል ናቸው። ምናሴ በሌላ መነጽር ብናየው የመንግሥት ቢሮክራት የመካከለኛው መደብ ውክል ነው። ሀገሩ ከንጉሣዊ ሥርዓት ወደ ወታደራዊ ሥርዓት ቢቀየርም፤ ከወታደራዊ ሥርዓት ወደ ሌላ ሥርዓት ቢለወጥም ምናሴያውያን ግን አይቀየሩም። ሥርዓት ይቀየራል - ምናሴያውያን አይቀየሩም፣ ትእዛዝ ይፈጽማሉ፣ ይከድራሉ። ይህ በኢትዮጵያ ፖለቲካል-ታሪክ ውስጥ የተደጋገመ፣ ግን ደግሞ ያልተስተዋለ እውነት ነው።
ሄላም የወታደር ልጅ ናት፤ እንዲያሳድጋት በአደራ የተሰጠው ቤተሰብ የሚበድላት። የሷ ዓይነት ዕጣ ከደረሰው እንደ ወንድሟ ከምታየው ቴዲ ከሚባል ልጅ ጋር ታድጋለች። መጀመሪያ የሚልዮን፣ የኋላ ኋላ የምናሴ ፍቅረኛ የምትኾን ድምፀ-መረዋ ሴት ናት። ሁሉ ነገሯን ባጣችበት ወቅት ጡቷ ተአምር ያመርታል።
በመዝሙረ ሄላም ላይ የሄላም የጡት ወተት የአንዳች ነገር ውክል ይመስለኛል። ሻዕቢያ ለታጋይ ወጣቶች ማሳደጊያ ፈልጓት ሊሰርቃት መፈለጉ በቀላሉ የሚዘለል ነገር ነው? ወተት እና ጡት በመጀመሪያ እይታ የሕፃናት ትዝታ፣ የእናትነት ምሥል፣ የእምነት እና የጾታ መነሳሳት የተዋሃዱበትም አይደል? ወተት ሕይወት ነው? የመጀመሪያ ምግብ፣ ከእናት ወደ ልጅ የሚፈስም አይደል? በክርስቲያናዊ ምልክት ንጹሕነትን አይወክልም? ወተት ከ“ቅዱስ” ወደ “ሥጋዊ” የሚያስተላልፍ ድልድይ ነው ማለት እንችል ይኾን? የሄላምን ጡት የጠባ ታማሚ ልጅ እንዴት ጤናማ ሊኾን ቻለ? የምን ትእምርት ነው? ሄላም ከብዙ ወንድ ጋር የወጣች እንደመኾኗ ለዚህ ሰናይ ግብር ለምን የሷ ጡት ተመረጠ?
ሌላው፣ መዝሙረ ሄላም ላይ ኦልቬቲን እናገኛታለን። ኦልቬቲ የግራጫ ቃጭልዋ። መዝገቡ ንፋስ መውጫ ሳለ፣ ባልንጀራው ኤልያስ የብልግና ሀሁ ሊያስተምረው እፊቱ ያቆማት ቀይ ሰሌዳ ነበረች ኦልቬቲ። መዝሙረ ሄላም ላይ ምናሴን እና ቤተሰቡን የምታሾር ዐውራ ገጸባሕርይ ኾና ትከሰታለች። መዝሙረ ሄላም እና ግራጫ ቃጭሎች በጋለሞታይቱ በኦልቬቲ ብቻ ሳይኾን በዘመነ እንድርያስ እና በመዝገቡ ዱባለም ይገናኛሉ። ነጋ ዳቦ ጋጋሪውም በ-typological space መዝሙረ ሄላም ላይ እናገኘዋለን።
መዝሙረ ሄላምን ከህላዌነት (Existentialism) አንጻር እንመልከተው። ሄላም ትርጉም በማይሰጥ ዓለም ውስጥ እንዴት እንደምትኖር እናነባለን። የሀገሯ ዳር ድንበር እንዳይነካ አባት ብታዋጣም አሳዳጊዎቿ ግን የወላጅን ፍቅር አዋጥተው አይለግሷትም። ወርቅ አበድራ ጠጠር ትነፈጋለች። ዕቃ ለማገዝ ቤቷ ድረስ ለመጣው ሚልዮን ልቧን ትሰጣለች። ሀና የሸነቆረችውን ክፍተት ለሞላችበት ውለታዋ ክፍያ ይኾን ዘንድ ሚልዮን ለሄላም የወለፈንዴ ቡጢ ያሳርፍባታል። ለሕይወት ትርጉም ለመስጠት ባስ ውስጥ ካገኘችው ሄኖክ ጋር ብትሞክርም የበለጠ የሕይወት ትርጉም ይዛባባታል። የወታደር ልጅ መኾኗ ሄላምነቷን በዜሮ ያባዘዋል። የመጨረሻው ስንብትም ከሄኖክ ጓደኛ አፎት በሚወጣ ሰይፍ መቀላት ይኾናል። ከሄኖክ ጓደኛ ጀርባ የሚውለበለበው ባንዲራ ደግሞ የሄኖክ ሸሚዝ መኾኑ ደግሞ ቁስሉን እንደ አቡሰዲቅ ያደርገዋል። ለሕይወቷ ትልቅ ትርጉም ያለውን የሙዚቃ ሥራዋን፣ “ትርጉም ወዳለው
ነገር ይቀይርልኛል” ብላ በምትተማመንበት በምናሴ ትነጠቃለች። ተአምር በሚያስብለው በጡት ወተት ምክንያት ለሕይወቷ ትርጉም ለመስጠት ትታትራለች። የጡት ወተቷን ምርምር በማድረግ ለትልቅ ዓለምአቀፍ በጎ ተፅዕኖ ታደርጋለች ተብላ የተቆጠረችው ሥዕለማርያም የዓለም አቀፍ መሳለቂያና ትችት ምንጭ ትኾንባታለች። ይህ ሁሉ ትርጉም የሌለው ድግግሞሽ ነው። ይህ ደግሞ በሳርተር የተገለጸውን “existence without essence”-ን ያሳያል።
የህላዌነት መሠረታዊ ሐሳብ ነጻነት ነው፤ ግን ነጻነት ፍርሃትን ይወልዳል። ሄላም ለአሮን ፍቅሯን መናገር ትችላለች፤ ነገር ግን ዝምታን መርጣለች። የግራጫው መዝገቡ፣ የእንጀራ እናቱ የምታደርስበትን በደል እንደሚያውቀው ሁሉ ሄላምም ክብካብና ዘበናይ የሚያደርሱባትን አድሎ ታውቃለች፤ ግን ለረዥም ጊዜ ዝም ብላለች። ሄላም፣ ሙዚቃዋን ካጣች በኋላ ወደ ባንዱ ሄዳ መጋፈጥ ትችላለች፤ ነገር ግን አትሄድም … ይህ በሳርተርኛ bad faith ነው።
የሄላም ምርጫ ዝምታ ኾነ እንጂ ደካማ ናት ማለት አይደለም። “አልተናገርኩም ማለት አላውቀውም ማለት አይደለም” የሚል ዝምታ ነው ያላት። በሌላ ጎኑ ደግሞ ዝምታዋ፣ የለመደችውን ግፍ ከማታውቀው ዐዲስ ግፍ የመምረጥ ኹኔታ ነው። ዐዳዲስ ግፎችን ለመሸሽ በዝምታ አላዋቂነት ዛጎል ውስጥ የመደበቅ ብቃት ነው። የለመደችውን ግፍ የመከላከል አቅም ስላላት ባለመደችው ግፍ እንዳያጠፏት ሠግታ በውስጣዊ ንቃተ ሕሊና የዘየደችው ብልሃት ሊኾን ይችላል። ዝምታዋ የመቆየቷ ምሥጢር ነው። ደበበ ቀዝቃዛ ገለልተኛ ነኝ የሚለው ሰው ለመኖር ሲል ሳይታወቀው ስሜቱን የሚቆጣጠርበት መንገድን ለማስታወስ ነው።
“የስንብት ቀለማት” ገጸባሕርይ የኾነው ዮሴፍም ብዙ ነገር ያውቃል፤ ግን ዝም ይላል … ፊያሜታ ቂል መስሏት ትዘባርቃለች … እሱ ግን “አልተናገርኩም ማለት አላውቀውም ማለት አይደለም” የሚል የዝምታ መልስ ይመልስላታል። እሷ ግን ዝምታው አይገባትም። የ“ቀዳዳ”ው ደበበ እና “የስንብት …” ዮሴፍ ቀዳዳውን አይሞሉትም፤ እያዩት ይኖራሉ። ዶነሮች ጥሩ ፈንድ ሲለቁ ፊያሜታ ፕሮጀክቱን ለአሳምነው ትሰጠውና ዮሴፍን “ምን ዶነሮች እኮ ጠፉ ትለዋለች” … ዝም ይላል፤ ይታዘባል።
ቃል መሣሪያ ነበር፤ በዘመነ ደበበ፣ በዘመነ ዮሴፍ፣ በዘመነ ሄላም እና በዘመነ መዝገቡ ዱባለ ግን ቃል አደገኛ ኾኗል፤ ዝምታ ኹነኛ መጠጊያ ነው … ይህ ከደርግ በኋላ የተፈጠረ “traumatized literary silence” ማሳያ ነው። ስለኾነም ተራኪዎቹ (ደበበ፣ መዝገቡ፣ ዮሴፍ እና ሄላም) ለምን ዝም አሉ ሳይኾን "ዝምታን የሚያመነጭ ሥርዓት ምን ይኾን?" ብለን እንድንጠይቅ ያደርጋል። ግለሰብ ዝም ሲል፤ ሕዝብ በጸጥታ ይዋጣል፤ የዚያኔ የተማከለው ኃይል አፍ ያወጣል።
የአዳምን ዐዲሱን መጽሐፍ "በንባብ ይለቅ" ብለን መርቀናል።
ቢኒያም አቡራ
ሐምሌ 25 / 2018 ዓ.ም
ከቢኒያም አቡራ
#ethiopia | አዳም ረታ ታሪክን ከነገሥታት፣ ከመሪዎች፣ ማኅበረሰቡ ባበጀው ድልድል ውስጥ ‹ላዕላይ› ከሚባሉት ደረጃዎች አንጻር አያስመለክተንም። ታሪካዊ ከሚባሉ አጋጣሚዎች ውስጥ የተዘነጉትን ጥቃቅን የታሪክ ኹነተ-ደቂቅ (micro-events) ይመርጣል። ይወስዳል መንገድ ላይ … “ቀዳዳ” በተሰኘው ታሪክ ላይ ፍንዳታውን ከሚሞት ዘመድ፣ ከሚደነግጥ ለማኝ፣ ከሚሰነጠቅ የወፍ እንቁላል፣ ከሚፈስ የእናት ወተት ጋር Micro-Macro Connection በመፍጠር የትልቁ ቀዳዳ መፈጠርን ከሚጢጢዬ ሽንቁሮች ጋር ያስተሳስርልናል። እንዲህ ያሉ የኒው ሂስቶሪሲዝም ባሕሪያትን ከዚህ ቀደም ባሳተማቸው መጻሕፍቱ ውስጥ በተለያየ መጠን እናገኛለን።
Adam Reta አዳም ረታ "መዝሙረ ሄላም" በተሰኘው በዐዲሱ መጽሐፉ ላይም በኢትዮጵያ ታሪካዊ-ፖለቲካዊ አጋጣሚ ውስጥ እንደ ዐውራ የሚታዩትን የእድገት በኅብረት ዘመቻን እንደነ-አሮን፣ እንደነቃል … ባሉ ገጸባሕርያት በኩል፣ የሰባ ሰባቱን ድርቅ በሄላም ጡት በኩል፣ “ጥላሁን ለምን ለምን ሞተ” እየተባለ ኢዮቤልዩ ቤተመንግሥት ጋር የተደረገውን ሰላማዊ ሰልፍ በሡልጣን በኩል፣ የከተማ መሬት ዐዋጅን በተለያዩ ግለሰቦች በኩል … እናያለን። በዚህም የታሪክን ትልቅ ካርታ ለመረዳት የተረሱና የጠለሉ ታሪኮችን ይመረምራል። ስለዚህ ነቁጣዊ ማኅበራዊ ክስተቶችን ወደ ታሪክ ምኩራብ በማምጣት ከትልቁ የታሪክ ምሥል ጎን ያስተያያል። ይህ ደግሞ የኒው ሂስቶሪሲዝም ኹነኛ ማጠንጠኛ ነው።
ልክ “ይወስዳል መንገድ ያመጣል መንገድ …” በተሰኘው መጽሐፉ ውስጥ ባለው “የመንግሥቱ ጊዜ” በሚለው ድርሰት ውስጥ፣ ትልቁን “የታኅሣሥ ግርግር”ን እንደ መቼት አምጥቶ የተጻፈውና የተተኮረው ግን ኹነተ-ደቂቅ (micro-events) ላይ ነው። ስለግርማሜ ንዋይ፣ ስለኮሌኔል ወርቅነህ ገበየሁ፣ ሰለጄነራል ሙልጌታ ቡሊ አይደለም የሚያትተው። ስለአንድ ብላቴና ከእንቅልፍ መነሳት፣ ስለገበጣ ጨዋታ፣ ቤተክርስቲያን ውስጥ ሕፃናትን አሰብስቦ ‹ኪራላይሶን› የሚያስብል ካሕን፣ ስለመንደር ውስጥ ሐሜቶች፣ ስለግለሰቦች ፍርሃት፣ በአጋጣሚ ስላየው አስደናቂ አሞራ … ያወጋል። የታሪክ አጋጣሚ አምጥቶ በታሪክ ውስጥ ግለሰቦች ላይ ስለሚረብበው የታሪክ መንፈስ ያትታል። ልክ እንደዚሁ መዝሙረ ሄላም ላይም ጽሑፉ ታሪክን አያብራራም፤ ነገር ግን ታሪክ እንዴት በሰው ልብ ውስጥ እንደሚኖር ያሳያል። በዚህ ኹነተ-ደቂቅ (micro-event) ምክንያት በዘመኑ ላይ ያገነገነውን ባሕላዊ እምነትን፣ የሥልጣን መዋቅርን፣ የወል ግንዛቤን አጨንቁረን እንድንመለከት ያስችለናል።
ከመንግሥት ሼልፍ ላይ ሳይኾን ከግለሰብ ጀርባ ላይ የተወሰደው የአዳም የአጻጻፍ መንገድ ከኒው ሂስቶሪስዝም ጽንሰ-ሐሳቦች ጋር በአንድ መም ላይ የሚሄዱ ናቸው። መዝሙረ ሄላም የተሰኘው ዐዲሱ የአዳም ረታ መጽሐፍ የኒው ሂስቶሪሲዝም ባሕርያትን ይጋራል። አንዳንድ ነገሮችን በዓይን መመልከት ባይቻልም በግብሩ (ቁስ ላይ በሚያደርገው ግፊት) ግን ይታወቃል። በመዝሙረ ሄላም መጽሐፍ ውስጥም አንዳንድ ነገሮችን በቀጥታ ማየት ባንችልም ቅሉ እነርሱን የሚያሳይልንን ነገሮች ግን እንቃኛለን። ዘማች ወጣት ተማሪዎችን እናያለን፤ መንግሥትን፣ ሕግንና ኃይልን ግን በቀጥታ አንመለከትም። የተማከለ ኃይል አናይም ግን የገጸባሕርያቱ የፍርሃት ምንጭ ከተማከለ ኃይል ጋር የተያያዘ ቀጭን መስመር መኖሩን እናያለን። መንግሥትም ቢኾን በቀጥታ አይገባም፤ ነገር ግን ፍርሃት እንደ ሥርዓት ዘዋሪ (system driver) ይኾናል። እንደ ሚሸል ፉኮ አገላለጽ ኃይል ከተማከለ ሥርዓት የሚመነጭ ሳይኾን በየትኛውም ቦታና ጊዜ በፍርሃት፣ በልማድ፣ በንግግር … ሊከሰት የሚችል ሂደት አይደል?
መዝሙረ ሄላም ላይ ታሪክ እንደ “circulation of social energy” ቀርቧል። መዝሙረ ሄላም ላይ መረጃ ከመንግሥት አይመጣም፤ ከግለሰብ እንጂ። የከተማ መሬት ዐዋጅም ኾነ የተማሪዎች ዘመቻ በገጸባሕርያቱ ወሬ ውስጥ ነው የሚንቀረቀበው። ይህ የመረጃ ሥርዓት ኃይል ማን እንዳለው ማን እንደሌለው ያሳያል። እንግዲህ ይህ በፉኮኛ micro-power መኾኑ ነው። በመዝሙረ ሄላም ላይ ታሪክ እንደ ወሬ እንጂ እንደ ሰነድ አይቀርብም።
ወሬ የፍርሃት ቤንዚን ነው … ፍርሃት ደግሞ በዝምታ መሸበብን ይፈጥራል … የዝምታ አፈ-ሙቅ ደግሞ ኃይለኛው እንዳይታይ ያደርጋል … የተደራጀው ኃይል ጥፋትን ሊያደርስ ባሰበ ቁጥር የወሬ ቤንዚን ይጨምራል። ሰዎች በዕቅብተ-ንግግር ራሳቸውን ሲሸብቡ ደርዝ ያለው ሙግት ይኮሰምናል፣ ንግግር ሲጠፋ ያልታወቀ አደጋ ይከሰታል፣ ፍርሃትም ይጨምራል። ያልታወቀ አደጋ ደግሞ ከታወቀ አካል ይመጣል። ስለዚህ ጥንስሱ የሚጀምረው ከወሬ እንደኾነ ያስመለክተናል። አዳም በመዝሙረ ሄላም ላይ ታሪክን እንደ “circulation of social energy” ሲያቀርብ ፕሬዝዳንት፣ ጀነራል፣ ፕሮፌሰር የኾኑ ታሪክ ከላዕላይ ያስቀመጣቸው ሰዎች አያስፈልጉትም። በአንጻሩ ሄላም ለማን እንደሳመችው ተደርጎ ብርሃኔ ያስወራው ወሬ፣ የሄላም አባት ወታደር በመኾኑ ምክንያት በካሱ፣ በሄኖክ እናት የተነዛው ወሬ እና ሄላም ከሄኖክ ጋር የተቆራረጠችበት መንገድ እንዲሁም የሄላምን የጡት ወተት በተመለከተ የተነዛው ወሬን ይጠቀማል።
መዝሙረ ሄላምን ከድኅረ-ቅኝ-አገዛዝ የኂስ መንገድ አንጻር እንመልከተው።
እውን ቅኝ-ግዛት ተረት ኾኖ ቀርቷል? በፖለቲካ፣ በኢኮኖሚ፣ በሥነልቦና ረገድ የቅኝ አገዛዝ ዳናው ሙሉ ለሙሉ ጠፍቷል? አዳም በመዝሙረ ሄላም ጽሑፍ ውስጥ ከቅኝ-ግዛት በተወረሰ መዋቅር ምክንያት የተሰናከለን ሕይወት ሊያስመለክተን ይኾን?
“ከተሞች ከቅኝ ግዛት በኋላ ሁለት ዓይነት መልክ ይኖራቸዋል፤ ለጥቂቱ የተድላ፣ ለተቀረው ደግሞ የአሳር መንደር ይኾናሉ” ይላል ፍራንዝ ፋኖን። በመዝሙረ ሄላም ላይ እና “የቢሾፍቱ ልጆች ጥላሞት” የተሰኘው ድርሰት ላይም ይህንን ነው የምንመለከተው። “ይወስዳል መንገድ ያመጣል መንገድ …” በተሰኘው መጽሐፉ ውስጥ ካሉ ጽሑፎች መካከል “የቢሾፍቱ ልጆች ጥላ ሞት” አንዱ ነው። የቢሾፍቱ ልጆች ሆቴሉን ያዩታል፤ ግን አይገቡበትም። ሆቴሉ የሀገራቸው መሬት ላይ ነው፤ እነርሱ ግን ከሆቴሉ ውጭ ናቸው። መናፈሻው ውስጥ አንዲት የፈረንጅ ልጅ ጠግባ ለልጆቹ እንደ ውሻ ዳቦ ትወረውርላቸዋለች። አፈር ላይ የወደቀን ዳቦ አራግፈው ይመገባሉ። በገዛ ሐይቃቸው ዳር ላይ ናቸው፤ ሌሎች ግን በጀልባ እየተንሸራሸሩ ይንፈላሰሳሉ። ለፈረንጆቹ ያደረው ሞገስ የላንድሮቨር ተፈናጣጭ ኾኗል። ሌሎቹ ግን ከመኪናው ውጪ ናቸው። ሞገስ እንደ እነርሱ ሕጻን ቢኾንም ለፈረንጅ በማሸርገዱ የትምህርት ቤቱ ባለቤት ሲመስል ሌሎች ልጆች ግን በገዛ መምህራቸው ይብጠለጠላሉ። የቢሾፍቱ ልጆች፣ ነጻ በተባለች ሀገር እየኖሩ በቅኝ ግዛት ጥላ ይተዳደራሉ። የቢሾፍቱ ልጆች በገዛ መንደራቸው አካሉ በማይታይ የቅኝ ግዛት እጅ ይገፋሉ። ሞገስ አይናገርም፤ የሚናገርለት አለ። ልክ የቢሾፍቱ ልጆች ላይ በአንድ ከተማ ውስጥ ሁለት የከተማ ምሥል እንደምናገኘው ሁሉ “የስንብት ቀለማት” ላይም በአዲስ አበባ ውስጥ ሁለት የከተማ ምሥል እንመለከታለን። እንደ ዘድሬክ፣ ሳተርን፣ ከተስፋዬ ወደ አሸናፊ የተቀየሩ የድሎት ምሥሎች እና የእነምትክ ጉልት፣ የእትየ እልልታ የጉርሻ መሸጫ መስኮት ያሉ የእጦት ሥዕል እናገኛለን። መዝሙረ ሄላም ላይም እንዲህ ያለ በአንድ ከተማ ላይ የሁለት ምሥሎች አደባባይ እጀግ ብዙ ቦታ ይገኛል።
በሌላኛው የድኅረ-ቅኝ-ግዛት ኂስ (postcolonial criticism) መዝሙረ ሄላምን ስንመለከት መጀመሪያ ላይ “ፈረንጅ ሲያደንቀኝና ሲገረምብኝ የሰሙ የአገሬ ደነዞች በየተራ “ካላስ የኔ ጎሳ ናት” … እያሉ መሻማት ጀመሩ ትላለች - ሄላም። በኋላ ደግሞ በተነዛባት አጓጉል ወሬ … የሄላምን ጡት ንቀው፣ አንጓጥጠው፣ አባረዋት ሲያበቁ የፈረንጅ የዱቄት ወተትን ይመርጣሉ። ይህ በባሕላዊ ማንነትና በዘመናዊነት መካከል የሚዋልል ማኅበረሰብን ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ የድኅረ-ቅኝ-ግዛት አካል ነው። በሌሎቹ የአዳም ሥራዎች ውስጥ ድኅረ-ቅኝ-ግዛት አተያይ በቋንቋና በኪነ-ጥበብ ምርጫ ውስጥ እንዴት እንደሚንፀባረቅ ያሳያል። በመዝሙረ ሄላም ላይ ደግሞ ምዕራባዊው ዓለም ለአገር በቀል መፍትኼ-ሥራይ የሚሰጠው ዋጋ ዝቅተኛ መኾኑንና የኢኮኖሚ ብዝበዛው አሁንም በረቂቅ መንገድ መቀጠሉን ያሳያል። እዚህ ላይ ሥዕለማርያም የተባለችዋን ገጸባሕርይ እና በውጭ ሀገራት የተነዙ ወሬዎችን ስንጨማምር ደግሞ የበለጠ ብዙ ለማለት ያስችላል።
መዝሙረ ሄላም ላይ እጅግ ብዙ ማኅበረሰባዊ ኂስ እናገኛለን። ለአብነት ያህል አንድ ሁለቱን እንቃኝ።
“መዝሙረ ሄላም” ላይ ማኅበረሰቡ በችላ-ባይነት አልያም በኾን ተብሎነት ልጆቹን ምን ያህል ተጠቂ እንዳደረጋቸው የሚያሳይ መልክ ተንጸባርቆበታል ማለት ይቻላል። ጋሽ ክብካብና ዘመናይ ኾን ብለው ቴዲና ሄላም ላይ የሚያደርሱትን፣ ተክለማርያም የወላጁን(የዘሪቱን) ችላ-ባይነት ለአብነት ማቅረብ ይቻላል። ማኅበረሰቡ ልጆችን “የነገ ተስፋዎች” ይላል፤ ነገር ግን ዛሬያቸው ላይ አይሠራም።
ማኅበረሰብ የመማጸኛ ከተማዎችን ወደ ተጨማሪ ግፍ መሥሪያ ቦታዎች እንደሚቀይር በአዳም መጻሕፍት ላይ በብዛት እንመለከታለን። “ይወስዳል መንገድ …” ላይ … “ቀዳዳ” በተሰኘው ታሪክ ላይ ማርታ ለደበበ በምትሰጠው ፍቅር ሳቢያ የሚሠራበትን ግፍ የምታስረሳ ብትኾንም ማኅበረሰቡ ግን ተጨማሪ ግፍ የሚሠራበት መሣሪያ ኾናለች። የስንብት ቀለማት ላይ ምኒልክ ከዚያ ሁሉ እስርና እንግልት በኋላ፣ “በፊያሜታ አርፋለሁ” ብሎ ቤቷ ሲሄድ ተጨማሪ ሕመም በጆሮው በኩል ጭንቅላቱ ላይ ይሻጥበታል። መዝሙረ ሄላም ላይም፣ ሄላም “ሙዚቃዬን ከሕዝብ ጆሮ ያደርስልኛል … ያሳርፈኛል …” ብላ የተመካችበት ምናሴ እንጦሮጦስ ይጨምራታል። ማኅበረሰባችን የመስቀል ተ ሠላጢን ግብር እንዳለው፣ ከላይ አሳልሞ ከታች በአንካሴው ጉድጓድ እንደሚምስ ያሳያል። ይህም የመልእክትን ወጭት ሰብሮ የወጣ ጥበባዊ አጻጻፍ ነው። በፈጣጣው የቀረበ የትችት ኮሶ አይደለም። ድንቅ ነው!
መዝሙረ ሄላም ላይ ከምናገኛቸው ዋና ዋና ገጸባሕርያት የተወሰኑት (አሮን፣ ቃል፣ ምናሴ፣ ሄላም) ላይ መጠነኛ ቅኝት እናድርግ።
auto-fiction ዓይነት አጻጻፍ ባለው የአሮን አተራረክ ውስጥ አሮን “system observer” መኾኑን እንገነዘባለን። ሥርዓቱን ያያል፣ ዘማቹን ያስተውላል፣ ቃለጉባኤ ይይዛል፣ ችግሩን ይመለከታል፣ ይጽፋል። አሮን የተገፋ ታሪክ ድምፅ ነው፤ ንቃት አለው፣ ግን የታሪክ ሂደትን የሚቀይር ኃይል የለውም፤ ስለዚህም ያ ሁሉ የጻፈውን ጽሑፍን ያጣል። የንቃት ችግር የለበትም፤ የማኅበራዊ ንቃት ድምፅነቱን ከዘመነ አባት ጋር ባደረገው ውይይት ውስጥ ተመልክተናል። ግን ደግሞ ይህ ብቻውን የቆመ ነጠላ ነገር ነው፤ ምክንያቱም ማኅበራዊ ተሳትፎ የለበትም። ቃል የተሰኘችው ገጸባሕርይም እንደ አሮን ናት፤ ንቃት ያላት፣ system observer ናት። ማኅበራዊ ንቃት ማኅበራዊ እንቅስቃሴ ካላገዘው ግንጥል ጌጥ ነው። ቃልና አሮን ንቃት አላቸው፤ ግን ንቃታቸውን ተግባር አላገዘውም፤ ንቃቱን የሚተገብር አደረጃጀት የላቸውም። ስለዚህ ዕጣ-ፈንታቸው ውድቀት ይኾናል። በኢትዮጵያ ውስጥ የተንሰራፋውን ይህን የድግግሞሽ አዙሪት መዝሙረ ሄላም ላይ ደራሲ አዳም ረታ በሰላ ብዕር አስቀምጧል።
የደራሲና የአርታኢ ትስስር በተንጸባረቀበት በሄላም አተራረክ ውስጥ ምናሴ የተሰኘ ገጸባሕርይ እናገኛለን። ምናሴ የ-false collective consciousness ትእምርት ነው። ምናሴዎች ለሥልጣን ይሠራሉ፣ ራሳቸውን እንደ ነጻ ያስባሉ፤ ነገር ግን የሥርዓቱ የመጠቀሚያ መሣሪያ (system functionary) ናቸው። ምናሴዎች የኦልቪቴዎች ጥይት ናቸው። ምናሴዎች የሔላምዎች ስኬት ሳይኾን የገዛ ጥቅማቸውን የሚያስቀድሙ የማኅበረሰቡ አካል ናቸው። ምናሴ በሌላ መነጽር ብናየው የመንግሥት ቢሮክራት የመካከለኛው መደብ ውክል ነው። ሀገሩ ከንጉሣዊ ሥርዓት ወደ ወታደራዊ ሥርዓት ቢቀየርም፤ ከወታደራዊ ሥርዓት ወደ ሌላ ሥርዓት ቢለወጥም ምናሴያውያን ግን አይቀየሩም። ሥርዓት ይቀየራል - ምናሴያውያን አይቀየሩም፣ ትእዛዝ ይፈጽማሉ፣ ይከድራሉ። ይህ በኢትዮጵያ ፖለቲካል-ታሪክ ውስጥ የተደጋገመ፣ ግን ደግሞ ያልተስተዋለ እውነት ነው።
ሄላም የወታደር ልጅ ናት፤ እንዲያሳድጋት በአደራ የተሰጠው ቤተሰብ የሚበድላት። የሷ ዓይነት ዕጣ ከደረሰው እንደ ወንድሟ ከምታየው ቴዲ ከሚባል ልጅ ጋር ታድጋለች። መጀመሪያ የሚልዮን፣ የኋላ ኋላ የምናሴ ፍቅረኛ የምትኾን ድምፀ-መረዋ ሴት ናት። ሁሉ ነገሯን ባጣችበት ወቅት ጡቷ ተአምር ያመርታል።
በመዝሙረ ሄላም ላይ የሄላም የጡት ወተት የአንዳች ነገር ውክል ይመስለኛል። ሻዕቢያ ለታጋይ ወጣቶች ማሳደጊያ ፈልጓት ሊሰርቃት መፈለጉ በቀላሉ የሚዘለል ነገር ነው? ወተት እና ጡት በመጀመሪያ እይታ የሕፃናት ትዝታ፣ የእናትነት ምሥል፣ የእምነት እና የጾታ መነሳሳት የተዋሃዱበትም አይደል? ወተት ሕይወት ነው? የመጀመሪያ ምግብ፣ ከእናት ወደ ልጅ የሚፈስም አይደል? በክርስቲያናዊ ምልክት ንጹሕነትን አይወክልም? ወተት ከ“ቅዱስ” ወደ “ሥጋዊ” የሚያስተላልፍ ድልድይ ነው ማለት እንችል ይኾን? የሄላምን ጡት የጠባ ታማሚ ልጅ እንዴት ጤናማ ሊኾን ቻለ? የምን ትእምርት ነው? ሄላም ከብዙ ወንድ ጋር የወጣች እንደመኾኗ ለዚህ ሰናይ ግብር ለምን የሷ ጡት ተመረጠ?
ሌላው፣ መዝሙረ ሄላም ላይ ኦልቬቲን እናገኛታለን። ኦልቬቲ የግራጫ ቃጭልዋ። መዝገቡ ንፋስ መውጫ ሳለ፣ ባልንጀራው ኤልያስ የብልግና ሀሁ ሊያስተምረው እፊቱ ያቆማት ቀይ ሰሌዳ ነበረች ኦልቬቲ። መዝሙረ ሄላም ላይ ምናሴን እና ቤተሰቡን የምታሾር ዐውራ ገጸባሕርይ ኾና ትከሰታለች። መዝሙረ ሄላም እና ግራጫ ቃጭሎች በጋለሞታይቱ በኦልቬቲ ብቻ ሳይኾን በዘመነ እንድርያስ እና በመዝገቡ ዱባለም ይገናኛሉ። ነጋ ዳቦ ጋጋሪውም በ-typological space መዝሙረ ሄላም ላይ እናገኘዋለን።
መዝሙረ ሄላምን ከህላዌነት (Existentialism) አንጻር እንመልከተው። ሄላም ትርጉም በማይሰጥ ዓለም ውስጥ እንዴት እንደምትኖር እናነባለን። የሀገሯ ዳር ድንበር እንዳይነካ አባት ብታዋጣም አሳዳጊዎቿ ግን የወላጅን ፍቅር አዋጥተው አይለግሷትም። ወርቅ አበድራ ጠጠር ትነፈጋለች። ዕቃ ለማገዝ ቤቷ ድረስ ለመጣው ሚልዮን ልቧን ትሰጣለች። ሀና የሸነቆረችውን ክፍተት ለሞላችበት ውለታዋ ክፍያ ይኾን ዘንድ ሚልዮን ለሄላም የወለፈንዴ ቡጢ ያሳርፍባታል። ለሕይወት ትርጉም ለመስጠት ባስ ውስጥ ካገኘችው ሄኖክ ጋር ብትሞክርም የበለጠ የሕይወት ትርጉም ይዛባባታል። የወታደር ልጅ መኾኗ ሄላምነቷን በዜሮ ያባዘዋል። የመጨረሻው ስንብትም ከሄኖክ ጓደኛ አፎት በሚወጣ ሰይፍ መቀላት ይኾናል። ከሄኖክ ጓደኛ ጀርባ የሚውለበለበው ባንዲራ ደግሞ የሄኖክ ሸሚዝ መኾኑ ደግሞ ቁስሉን እንደ አቡሰዲቅ ያደርገዋል። ለሕይወቷ ትልቅ ትርጉም ያለውን የሙዚቃ ሥራዋን፣ “ትርጉም ወዳለው
ነገር ይቀይርልኛል” ብላ በምትተማመንበት በምናሴ ትነጠቃለች። ተአምር በሚያስብለው በጡት ወተት ምክንያት ለሕይወቷ ትርጉም ለመስጠት ትታትራለች። የጡት ወተቷን ምርምር በማድረግ ለትልቅ ዓለምአቀፍ በጎ ተፅዕኖ ታደርጋለች ተብላ የተቆጠረችው ሥዕለማርያም የዓለም አቀፍ መሳለቂያና ትችት ምንጭ ትኾንባታለች። ይህ ሁሉ ትርጉም የሌለው ድግግሞሽ ነው። ይህ ደግሞ በሳርተር የተገለጸውን “existence without essence”-ን ያሳያል።
የህላዌነት መሠረታዊ ሐሳብ ነጻነት ነው፤ ግን ነጻነት ፍርሃትን ይወልዳል። ሄላም ለአሮን ፍቅሯን መናገር ትችላለች፤ ነገር ግን ዝምታን መርጣለች። የግራጫው መዝገቡ፣ የእንጀራ እናቱ የምታደርስበትን በደል እንደሚያውቀው ሁሉ ሄላምም ክብካብና ዘበናይ የሚያደርሱባትን አድሎ ታውቃለች፤ ግን ለረዥም ጊዜ ዝም ብላለች። ሄላም፣ ሙዚቃዋን ካጣች በኋላ ወደ ባንዱ ሄዳ መጋፈጥ ትችላለች፤ ነገር ግን አትሄድም … ይህ በሳርተርኛ bad faith ነው።
የሄላም ምርጫ ዝምታ ኾነ እንጂ ደካማ ናት ማለት አይደለም። “አልተናገርኩም ማለት አላውቀውም ማለት አይደለም” የሚል ዝምታ ነው ያላት። በሌላ ጎኑ ደግሞ ዝምታዋ፣ የለመደችውን ግፍ ከማታውቀው ዐዲስ ግፍ የመምረጥ ኹኔታ ነው። ዐዳዲስ ግፎችን ለመሸሽ በዝምታ አላዋቂነት ዛጎል ውስጥ የመደበቅ ብቃት ነው። የለመደችውን ግፍ የመከላከል አቅም ስላላት ባለመደችው ግፍ እንዳያጠፏት ሠግታ በውስጣዊ ንቃተ ሕሊና የዘየደችው ብልሃት ሊኾን ይችላል። ዝምታዋ የመቆየቷ ምሥጢር ነው። ደበበ ቀዝቃዛ ገለልተኛ ነኝ የሚለው ሰው ለመኖር ሲል ሳይታወቀው ስሜቱን የሚቆጣጠርበት መንገድን ለማስታወስ ነው።
“የስንብት ቀለማት” ገጸባሕርይ የኾነው ዮሴፍም ብዙ ነገር ያውቃል፤ ግን ዝም ይላል … ፊያሜታ ቂል መስሏት ትዘባርቃለች … እሱ ግን “አልተናገርኩም ማለት አላውቀውም ማለት አይደለም” የሚል የዝምታ መልስ ይመልስላታል። እሷ ግን ዝምታው አይገባትም። የ“ቀዳዳ”ው ደበበ እና “የስንብት …” ዮሴፍ ቀዳዳውን አይሞሉትም፤ እያዩት ይኖራሉ። ዶነሮች ጥሩ ፈንድ ሲለቁ ፊያሜታ ፕሮጀክቱን ለአሳምነው ትሰጠውና ዮሴፍን “ምን ዶነሮች እኮ ጠፉ ትለዋለች” … ዝም ይላል፤ ይታዘባል።
ቃል መሣሪያ ነበር፤ በዘመነ ደበበ፣ በዘመነ ዮሴፍ፣ በዘመነ ሄላም እና በዘመነ መዝገቡ ዱባለ ግን ቃል አደገኛ ኾኗል፤ ዝምታ ኹነኛ መጠጊያ ነው … ይህ ከደርግ በኋላ የተፈጠረ “traumatized literary silence” ማሳያ ነው። ስለኾነም ተራኪዎቹ (ደበበ፣ መዝገቡ፣ ዮሴፍ እና ሄላም) ለምን ዝም አሉ ሳይኾን "ዝምታን የሚያመነጭ ሥርዓት ምን ይኾን?" ብለን እንድንጠይቅ ያደርጋል። ግለሰብ ዝም ሲል፤ ሕዝብ በጸጥታ ይዋጣል፤ የዚያኔ የተማከለው ኃይል አፍ ያወጣል።
የአዳምን ዐዲሱን መጽሐፍ "በንባብ ይለቅ" ብለን መርቀናል።
ቢኒያም አቡራ
ሐምሌ 25 / 2018 ዓ.ም
1 day ago
የጨጓራ ህመም ተገቢዉን ህክምና ካላገኘ የምግብ መተላለፊያ ቱቦን በመዝጋት ለከፋ የጤና ችግር ሊያጋልጥ ይችላል ተባለ
የጨጓራ ህመምን በቤት ዉስጥ በተለያዩ መንገዶች ማከም አንዱ አማራጭ ቢሆንም ደረጃዉ ከፍ ሳይል ተገቢዉን የህክምና አገልግሎት ካላገኘ ለከፋ የጤና ችግር እንደሚያጋልጥ ተገልጿል።የጨጓራ ህመም ተገቢዉን የህክምና እርዳታ ካላገኘ እና ወደ መጨረሻዉ ደረጃ ከፍ ካለ ቁስለቱ እስከ መድማት ደርሶ ደም ማስመለስን ሊያስከትል ይችላል ።
የጨጓራ ቁስለት በከፍተኛ ደረጃ ተባብሶ የጨጓራ ግድግዳን ሙሉ በሙሉ በመብሳት ቀዳዳ በሚፈጥርበት ወቅት በሆድ ዕቃ ውስጥ ከባድ ኢንፌክሽንን ስለሚያስከትል አስቸኳይ የሕክምና እርዳታ ማግኘት ተገቢ ነዉ ተብሏል ።በተጨማሪም ጨጓራ ከትንሹ አንጀት ጋር የሚገናኝበት ቦታ ላይ በተደጋጋሚ ጉዳት ሲደርስበት ቦታዉ ይጠብና የምግብ መተላለፊያ ቱቦን በመዝጋት ለከፋ የጤና ችግር ስለሚያጋልጥ ተገቢዉን የህክምና እገዛ ማድረግ አስፈላጊ እንደሆነ በየካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ የዉስጥ ደዌ ስፔሻሊስት ዶክተር አምደመስቀል መርሻ ከብስራት ሬዲዮ ጋር ባደረጉት ቆይታ ተናግረዋል ።
የህክምና ባለሙያው አክለዉም በአንዳንድ ሰዎች ላይ በጨጓራ ባክቴሪያ አማካኝነት ወደ ካንሰር የመቀየር ዕድል ሊኖረዉ እንደሚችል አስገንዝበዋል።ለህመም ማስታገሻ ተብለዉ የሚወሰዱ እንደ አይቡፕሮፌን እና አስፕሪን ያሉ መድሃኒቶች ለረጅም ጊዜ የሚወሰዱ ከሆነ ለጨጓራ ቁስለት ሊያጋልጡ ይችላሉ በማለት የህክምና ባለሙያው ጨምረው ለብስራት ሬድዮ ተናግረዋል።
Seledadotio
Seledadotio
የጨጓራ ህመምን በቤት ዉስጥ በተለያዩ መንገዶች ማከም አንዱ አማራጭ ቢሆንም ደረጃዉ ከፍ ሳይል ተገቢዉን የህክምና አገልግሎት ካላገኘ ለከፋ የጤና ችግር እንደሚያጋልጥ ተገልጿል።የጨጓራ ህመም ተገቢዉን የህክምና እርዳታ ካላገኘ እና ወደ መጨረሻዉ ደረጃ ከፍ ካለ ቁስለቱ እስከ መድማት ደርሶ ደም ማስመለስን ሊያስከትል ይችላል ።
የጨጓራ ቁስለት በከፍተኛ ደረጃ ተባብሶ የጨጓራ ግድግዳን ሙሉ በሙሉ በመብሳት ቀዳዳ በሚፈጥርበት ወቅት በሆድ ዕቃ ውስጥ ከባድ ኢንፌክሽንን ስለሚያስከትል አስቸኳይ የሕክምና እርዳታ ማግኘት ተገቢ ነዉ ተብሏል ።በተጨማሪም ጨጓራ ከትንሹ አንጀት ጋር የሚገናኝበት ቦታ ላይ በተደጋጋሚ ጉዳት ሲደርስበት ቦታዉ ይጠብና የምግብ መተላለፊያ ቱቦን በመዝጋት ለከፋ የጤና ችግር ስለሚያጋልጥ ተገቢዉን የህክምና እገዛ ማድረግ አስፈላጊ እንደሆነ በየካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ የዉስጥ ደዌ ስፔሻሊስት ዶክተር አምደመስቀል መርሻ ከብስራት ሬዲዮ ጋር ባደረጉት ቆይታ ተናግረዋል ።
የህክምና ባለሙያው አክለዉም በአንዳንድ ሰዎች ላይ በጨጓራ ባክቴሪያ አማካኝነት ወደ ካንሰር የመቀየር ዕድል ሊኖረዉ እንደሚችል አስገንዝበዋል።ለህመም ማስታገሻ ተብለዉ የሚወሰዱ እንደ አይቡፕሮፌን እና አስፕሪን ያሉ መድሃኒቶች ለረጅም ጊዜ የሚወሰዱ ከሆነ ለጨጓራ ቁስለት ሊያጋልጡ ይችላሉ በማለት የህክምና ባለሙያው ጨምረው ለብስራት ሬድዮ ተናግረዋል።
Seledadotio
Seledadotio
1 day ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የሚኒሶታ ጤና መምሪያ በግዛቲቱ በሚገኙ የሜክሲኮ ምግብ ቤቶች ውስጥ ከሚቀርበው ሃላፒኖ የሚባለው የቃሪያ ዓይነት (የሜክሲኮ ቃሪያ) ጋር የተያያዘ የ'ሳልሞኔላ ጃቪያና' ወረርሽኝን እየመረመረ መሆኑን አስታወቀ። መምሪያው እስካሁን 110 የተረጋገጡ የሳልሞኔላ ታማሚዎች መመዝገባቸውን ገልጿል።
የጤና ባለስልጣናት ህመሙ ከተከሰተባቸው ሰዎች መካከል 84ቱን ያነጋገሩ ሲሆን፣ ከእነዚህ ውስጥ 75 በመቶ የሚሆኑት ከሰኔ 14 እስከ ሀምሌ 14 ባለው ጊዜ ውስጥ 'ቺፖትሌ' በተባለው ታዋቂ ምግብ ቤት የተመገቡ መሆናቸውን ጠቁመዋል። ቀሪዎቹ ደግሞ በሌሎች የሜክሲኮ ምግብ ቤቶች መመገባቸውን ተናግረዋል። ወረርሽኙን ተከትሎ ቺፖትሌ በሚኒሶታ ከሚገኙ በርካታ ቅርንጫፎቹ ሃላፔኖ ቃሪያዎችን ማንሳቱን አስታውቋል።
የቺፖትሌ ቃል አቀባይ በሰጡት መግለጫ፣ "ሊከሰት ስለሚችለው ወረርሽኝ እንደሰማን ወዲያውኑ የክትትል ስርዓታችንን በመጠቀም ሃላፔኖ ቃሪያው የተሰራጨባቸውን ምግብ ቤቶች ለይተናል፤ ለጥንቃቄ ሲባልም የተጠረጠሩትን ምርቶች ከምግብ ቤቶቻችን በማስወገድ ከሌሎች አምራቾች በተገኙ ቃሪያዎች ተክተናል" ብለዋል። በሚኒሶታ ጤና መምሪያ የምግብ ወለድ በሽታዎች ክፍል ከፍተኛ ኤፒዲሚዮሎጂስት ካርሎታ ሜዱስ በበኩላቸው፣ ቺፖትሌ ከምርመራው ጋር በተያያዘ መረጃዎችን ከመስጠት ጀምሮ የተጠረጠሩትን ቃሪያዎች ለማስወገድ የወሰደውን ፈጣን እርምጃ በማንሳት የተቋሙን ሙሉ ትብብር አድንቀዋል።
የጤና መምሪያው ወረርሽኙ አሁንም እንደቀጠለ ለማወቅ ጊዜው ገና መሆኑን ቢገልጽም፣ ቺፖትሌ በወሰደው ፈጣን እርምጃ ምክንያት በድርጅቱ ላይ ስጋት እንደሌለው አስታውቋል። ሆኖም የተበከለው ቃሪያ በሌሎች ምግብ ቤቶች አሁንም እየቀረበ ከሆነ ወረርሽኙ ሊቀጥል እንደሚችል እና በቀጣይ ቀናት ተጨማሪ ታማሚዎች ሊመዘገቡ እንደሚችሉ ስጋቱን አጋርቷል።
ወረርሽኙን በፍጥነት ለመቆጣጠር የታማሚዎች መረጃ እጅግ ወሳኝ መሆኑን የገለጹት ካርሎታ ሜዱስ፣ የጤና ባለሙያዎች ምርመራቸውን የሚያካሂዱት ጥቆማ በደረሳቸው ታማሚዎች ላይ በመደወል በመሆኑ፣ ህብረተሰቡ ለሚደረጉ የስልክ ጥሪዎች ምላሽ በመስጠት ትብብር እንዲያደርግ ጥሪያቸውን አቅርበዋል።
የጤና ባለስልጣናት ህመሙ ከተከሰተባቸው ሰዎች መካከል 84ቱን ያነጋገሩ ሲሆን፣ ከእነዚህ ውስጥ 75 በመቶ የሚሆኑት ከሰኔ 14 እስከ ሀምሌ 14 ባለው ጊዜ ውስጥ 'ቺፖትሌ' በተባለው ታዋቂ ምግብ ቤት የተመገቡ መሆናቸውን ጠቁመዋል። ቀሪዎቹ ደግሞ በሌሎች የሜክሲኮ ምግብ ቤቶች መመገባቸውን ተናግረዋል። ወረርሽኙን ተከትሎ ቺፖትሌ በሚኒሶታ ከሚገኙ በርካታ ቅርንጫፎቹ ሃላፔኖ ቃሪያዎችን ማንሳቱን አስታውቋል።
የቺፖትሌ ቃል አቀባይ በሰጡት መግለጫ፣ "ሊከሰት ስለሚችለው ወረርሽኝ እንደሰማን ወዲያውኑ የክትትል ስርዓታችንን በመጠቀም ሃላፔኖ ቃሪያው የተሰራጨባቸውን ምግብ ቤቶች ለይተናል፤ ለጥንቃቄ ሲባልም የተጠረጠሩትን ምርቶች ከምግብ ቤቶቻችን በማስወገድ ከሌሎች አምራቾች በተገኙ ቃሪያዎች ተክተናል" ብለዋል። በሚኒሶታ ጤና መምሪያ የምግብ ወለድ በሽታዎች ክፍል ከፍተኛ ኤፒዲሚዮሎጂስት ካርሎታ ሜዱስ በበኩላቸው፣ ቺፖትሌ ከምርመራው ጋር በተያያዘ መረጃዎችን ከመስጠት ጀምሮ የተጠረጠሩትን ቃሪያዎች ለማስወገድ የወሰደውን ፈጣን እርምጃ በማንሳት የተቋሙን ሙሉ ትብብር አድንቀዋል።
የጤና መምሪያው ወረርሽኙ አሁንም እንደቀጠለ ለማወቅ ጊዜው ገና መሆኑን ቢገልጽም፣ ቺፖትሌ በወሰደው ፈጣን እርምጃ ምክንያት በድርጅቱ ላይ ስጋት እንደሌለው አስታውቋል። ሆኖም የተበከለው ቃሪያ በሌሎች ምግብ ቤቶች አሁንም እየቀረበ ከሆነ ወረርሽኙ ሊቀጥል እንደሚችል እና በቀጣይ ቀናት ተጨማሪ ታማሚዎች ሊመዘገቡ እንደሚችሉ ስጋቱን አጋርቷል።
ወረርሽኙን በፍጥነት ለመቆጣጠር የታማሚዎች መረጃ እጅግ ወሳኝ መሆኑን የገለጹት ካርሎታ ሜዱስ፣ የጤና ባለሙያዎች ምርመራቸውን የሚያካሂዱት ጥቆማ በደረሳቸው ታማሚዎች ላይ በመደወል በመሆኑ፣ ህብረተሰቡ ለሚደረጉ የስልክ ጥሪዎች ምላሽ በመስጠት ትብብር እንዲያደርግ ጥሪያቸውን አቅርበዋል።
Sponsored by
Surafel
2 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የቀድሞው የዓለም ባንክ ፕሬዝዳንት ዴቪድ ማልፓስን ሀሳብ ዋቢ በማድረግ ክቡር ገና ባወጡት ትንታኔ፣ በኢትዮጵያ እየተተገበረ ያለው የኢኮኖሚ ማሻሻያ እና የገንዘብ ፖሊሲ በተራው ዜጋ ላይ እያስከተለ ያለውን ጫና በጽኑ ተችተዋል። የኢኮኖሚ ቃላቶች እንደ "ማረጋጋት"፣ "ሊበራላይዜሽን"፣ "የገበያ መተማመን" እና "ተለዋዋጭ የምንዛሬ ተመን" የመሳሰሉት ዘመናዊነትን እና ኃላፊነትን የሚያንፀባርቁ ቢመስሉም፣ ከዚህ መረጋጋት ተጠቃሚው ማነው የሚለው ጥያቄ ግን ክሪቲካል መሆኑን ጽሁፉ ያነሳል።
የኢትዮጵያ መንግስት የብርን የምንዛሬ ተመን በገበያ እንዲወሰን ማድረጉ የማይቀር አማራጭ እንደነበር ይከራከራል። ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ተቋማትም ይህንን በመደገፍ የውጭ ምንዛሪ ገበያው በነፃነት እየሰራ መምጣቱን፣ የወጪ ንግድ ገቢ መጨመሩን፣ የዋጋ ግሽበት ከነበረበት ከፍተኛ ደረጃ መጠነኛ መሻሻል ማሳየቱን፣ እንዲሁም የዕዳ ሽግሽግ ሂደቱ እርምጃ እያሳየ መሆኑን እንደ አበረታች ውጤቶች ይጠቅሳሉ። ይሁን እንጂ፣ እነዚህ ማሻሻያዎች የዜጎችን ድህነት እንዳባባሱ እና የተራውን ኢትዮጵያዊ የመግዛት አቅም በከፍተኛ ሁኔታ እንዳዳከሙ የቀድሞው የዓለም ባንክ ፕሬዝዳንት ሞግተዋል። ክቡር ገና በጽሁፋቸው እንዳስገነዘቡት፣ እነዚህ ሁለት ተቃራኒ የሚመስሉ ሀሳቦች ስኬትን ከሚለኩበት መነፅር አንፃር የሚለያዩ እንጂ የሚጣረሱ አይደሉም። አንደኛው የማክሮ ኢኮኖሚ ተቋማትን ጤንነት ሲለካ፣ ሌላኛው ደግሞ የህብረተሰቡን ተጨባጭ የኑሮ ሁኔታ ይለካል።
አንድ ሀገር ያደገች የምትባለው የምንዛሬ ተመኗ በነፃ ገበያ ስለተመራ፣ የባለሀብቶች መተማመን ስለጨመረ ወይም የዕዳ ሽግሽግ ስለተደረገ አይደለም። እነዚህ ግቡን መምቻ መንገዶች እንጂ እራሳቸውን የቻሉ ግቦች አይደሉም። የጽሁፉ አቅራቢ እንዳስቀመጡት የእውነተኛ እድገት መለኪያዎች የምርት አቅም መስፋፋትን፣ የሰራተኞች ምርታማነት ማደግን፣ የኢንዱስትሪዎች አቅም መጎልበትን፣ የአርሶ አደሩ ምርት መጨመርን፣ ወጣቶች ትርጉም ያለው የስራ ዕድል ማግኘታቸውን፣ እንዲሁም ሀገሪቱ በውጭ ፋይናንስ ላይ ያላት ጥገኝነት መቀነሱን ያካትታሉ። ታሪክ እንደሚያስተምረው፣ የበለጸጉ ሀገራት መጀመሪያ ገበያቸውን በማስተካከል ሳይሆን፤ ምርታቸውን በማሳደግ፣ ስትራቴጂካዊ ኢንዱስትሪዎቻቸውን በመጠበቅ እና የቴክኖሎጂ አቅማቸውን በመገንባት ነው ሀብታም የሆኑት። ኢትዮጵያ ግን አሁን ላይ የፋይናንስ ማሻሻያውን በማስቀደም፣ መዋቅራዊ ሽግግሩን ወደ ኋላ በመተው የተገላቢጦሽ መንገድ እየተጓዘች መሆኗን ጽሁፉ ይተቻል።
የእነዚህን የኢኮኖሚ ማሻሻያዎች ጫና የሚሸከሙት ዓለም አቀፍ አበዳሪዎች፣ የፋይናንስ ተቋማት ወይም ሀብታቸው ዋጋ በሚጨምር ንብረቶች የተጠበቀላቸው አካላት አይደሉም። ይልቁንም የኢኮኖሚው ማሻሻያ ጫና በዋናነት የሚያርፈው በደመወዝ ተከፋዮች፣ በአነስተኛ የንግድ ተቋማት፣ በሸማቾች፣ ከውጭ የሚገቡ ግብዓቶችን ውድ በሆነ ዋጋ በሚገዙ አርሶ አደሮች፣ እና እጅግ ውድ ወደሆነው የስራ ገበያ አዲስ በሚቀላቀሉ ወጣቶች ላይ ነው። በመሆኑም እነዚህ የኢኮኖሚ ድንጋጤን የመቋቋም አቅም የሌላቸው የህብረተሰብ ክፍሎች፣ ለማክሮ ኢኮኖሚው መረጋጋት ዋነኛ ፋይናንስ አድራጊዎች ሆነዋል። ምንም እንኳን ይህ ጫና ጊዜያዊ መስዋዕትነት ተብሎ ቢቀርብም፣ ጊዜያዊ መስዋዕትነቶች ወደ ቋሚነት የመቀየር አዝማሚያ እንዳላቸው ታሪክ ያሳያል።
እርግጥ ነው የትኛውም ሀገር ስር በሰደደ የዋጋ ግሽበት፣ በተዛባ የምንዛሬ ተመን እና ሊቋቋመው በማይችለው የህዝብ ፋይናንስ ውስጥ ሆኖ ሊበለጽግ አይችልም። ነገር ግን ኢኮኖሚያዊ መረጋጋቱ የማንን ፍላጎት ለማሟላት ነው? መረጋጋቱ በራሱ ብቸኛ ግብ ከሆነ፣ ኢኮኖሚው ከልማት ቅድሚያዎች ይልቅ የፋይናንስ አመልካቾችን ወደ ማሟላት ይሸጋገራል። በውጤቱም፣ በጀቶች ጤናማ ሲሆኑ ቤተሰቦች እየደኸዩ ይሄዳሉ፤ የውጭ መተማመን ሲጨምር የሀገር ውስጥ የመግዛት አቅም ይዳከማል፤ በመጨረሻም የኢኮኖሚ ፖሊሲው ህዝብን ከማገልገል ይልቅ ገበያን እና አበዳሪዎችን ወደ ማርካት ይዞራል። የቀድሞው የዓለም ባንክ ፕሬዝዳንት ለማስታወስ እንደሞከሩት፤ የማክሮ ኢኮኖሚ ስኬት ማለት፣ ማህበራዊ ስኬት ማለት አይደለም። ታሪክ በመጨረሻ የሚጠይቀው ጥያቄ፣ ገበያው ቀልጣፋ መሆኑን፣ የምንዛሬ ተመኑ ተለዋዋጭ መሆኑን ወይም የዋጋ ግሽበቱ የታሰበው ግብ ላይ መድረሱን ሳይሆን ማሻሻያው ሀገሪቱን ከበፊቱ የበለጠ ጠንካራ አድርጓታል ወይ የሚለውን ነው። የማክሮ ኢኮኖሚ አመልካቾች እየተሻሻሉ ህዝቡ እየደኸየ የሚሄድባት ሀገር መረጋጋትን ልታመጣ ትችል ይሆናል፤ ነገር ግን እድገትን አምጥታለች ወይ የሚለው አሁንም ምላሽ ያላገኘ ትልቅ ጥያቄ መሆኑን ጽሁፉ በፅኑ ያስገነዝባል።
የኢትዮጵያ መንግስት የብርን የምንዛሬ ተመን በገበያ እንዲወሰን ማድረጉ የማይቀር አማራጭ እንደነበር ይከራከራል። ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ተቋማትም ይህንን በመደገፍ የውጭ ምንዛሪ ገበያው በነፃነት እየሰራ መምጣቱን፣ የወጪ ንግድ ገቢ መጨመሩን፣ የዋጋ ግሽበት ከነበረበት ከፍተኛ ደረጃ መጠነኛ መሻሻል ማሳየቱን፣ እንዲሁም የዕዳ ሽግሽግ ሂደቱ እርምጃ እያሳየ መሆኑን እንደ አበረታች ውጤቶች ይጠቅሳሉ። ይሁን እንጂ፣ እነዚህ ማሻሻያዎች የዜጎችን ድህነት እንዳባባሱ እና የተራውን ኢትዮጵያዊ የመግዛት አቅም በከፍተኛ ሁኔታ እንዳዳከሙ የቀድሞው የዓለም ባንክ ፕሬዝዳንት ሞግተዋል። ክቡር ገና በጽሁፋቸው እንዳስገነዘቡት፣ እነዚህ ሁለት ተቃራኒ የሚመስሉ ሀሳቦች ስኬትን ከሚለኩበት መነፅር አንፃር የሚለያዩ እንጂ የሚጣረሱ አይደሉም። አንደኛው የማክሮ ኢኮኖሚ ተቋማትን ጤንነት ሲለካ፣ ሌላኛው ደግሞ የህብረተሰቡን ተጨባጭ የኑሮ ሁኔታ ይለካል።
አንድ ሀገር ያደገች የምትባለው የምንዛሬ ተመኗ በነፃ ገበያ ስለተመራ፣ የባለሀብቶች መተማመን ስለጨመረ ወይም የዕዳ ሽግሽግ ስለተደረገ አይደለም። እነዚህ ግቡን መምቻ መንገዶች እንጂ እራሳቸውን የቻሉ ግቦች አይደሉም። የጽሁፉ አቅራቢ እንዳስቀመጡት የእውነተኛ እድገት መለኪያዎች የምርት አቅም መስፋፋትን፣ የሰራተኞች ምርታማነት ማደግን፣ የኢንዱስትሪዎች አቅም መጎልበትን፣ የአርሶ አደሩ ምርት መጨመርን፣ ወጣቶች ትርጉም ያለው የስራ ዕድል ማግኘታቸውን፣ እንዲሁም ሀገሪቱ በውጭ ፋይናንስ ላይ ያላት ጥገኝነት መቀነሱን ያካትታሉ። ታሪክ እንደሚያስተምረው፣ የበለጸጉ ሀገራት መጀመሪያ ገበያቸውን በማስተካከል ሳይሆን፤ ምርታቸውን በማሳደግ፣ ስትራቴጂካዊ ኢንዱስትሪዎቻቸውን በመጠበቅ እና የቴክኖሎጂ አቅማቸውን በመገንባት ነው ሀብታም የሆኑት። ኢትዮጵያ ግን አሁን ላይ የፋይናንስ ማሻሻያውን በማስቀደም፣ መዋቅራዊ ሽግግሩን ወደ ኋላ በመተው የተገላቢጦሽ መንገድ እየተጓዘች መሆኗን ጽሁፉ ይተቻል።
የእነዚህን የኢኮኖሚ ማሻሻያዎች ጫና የሚሸከሙት ዓለም አቀፍ አበዳሪዎች፣ የፋይናንስ ተቋማት ወይም ሀብታቸው ዋጋ በሚጨምር ንብረቶች የተጠበቀላቸው አካላት አይደሉም። ይልቁንም የኢኮኖሚው ማሻሻያ ጫና በዋናነት የሚያርፈው በደመወዝ ተከፋዮች፣ በአነስተኛ የንግድ ተቋማት፣ በሸማቾች፣ ከውጭ የሚገቡ ግብዓቶችን ውድ በሆነ ዋጋ በሚገዙ አርሶ አደሮች፣ እና እጅግ ውድ ወደሆነው የስራ ገበያ አዲስ በሚቀላቀሉ ወጣቶች ላይ ነው። በመሆኑም እነዚህ የኢኮኖሚ ድንጋጤን የመቋቋም አቅም የሌላቸው የህብረተሰብ ክፍሎች፣ ለማክሮ ኢኮኖሚው መረጋጋት ዋነኛ ፋይናንስ አድራጊዎች ሆነዋል። ምንም እንኳን ይህ ጫና ጊዜያዊ መስዋዕትነት ተብሎ ቢቀርብም፣ ጊዜያዊ መስዋዕትነቶች ወደ ቋሚነት የመቀየር አዝማሚያ እንዳላቸው ታሪክ ያሳያል።
እርግጥ ነው የትኛውም ሀገር ስር በሰደደ የዋጋ ግሽበት፣ በተዛባ የምንዛሬ ተመን እና ሊቋቋመው በማይችለው የህዝብ ፋይናንስ ውስጥ ሆኖ ሊበለጽግ አይችልም። ነገር ግን ኢኮኖሚያዊ መረጋጋቱ የማንን ፍላጎት ለማሟላት ነው? መረጋጋቱ በራሱ ብቸኛ ግብ ከሆነ፣ ኢኮኖሚው ከልማት ቅድሚያዎች ይልቅ የፋይናንስ አመልካቾችን ወደ ማሟላት ይሸጋገራል። በውጤቱም፣ በጀቶች ጤናማ ሲሆኑ ቤተሰቦች እየደኸዩ ይሄዳሉ፤ የውጭ መተማመን ሲጨምር የሀገር ውስጥ የመግዛት አቅም ይዳከማል፤ በመጨረሻም የኢኮኖሚ ፖሊሲው ህዝብን ከማገልገል ይልቅ ገበያን እና አበዳሪዎችን ወደ ማርካት ይዞራል። የቀድሞው የዓለም ባንክ ፕሬዝዳንት ለማስታወስ እንደሞከሩት፤ የማክሮ ኢኮኖሚ ስኬት ማለት፣ ማህበራዊ ስኬት ማለት አይደለም። ታሪክ በመጨረሻ የሚጠይቀው ጥያቄ፣ ገበያው ቀልጣፋ መሆኑን፣ የምንዛሬ ተመኑ ተለዋዋጭ መሆኑን ወይም የዋጋ ግሽበቱ የታሰበው ግብ ላይ መድረሱን ሳይሆን ማሻሻያው ሀገሪቱን ከበፊቱ የበለጠ ጠንካራ አድርጓታል ወይ የሚለውን ነው። የማክሮ ኢኮኖሚ አመልካቾች እየተሻሻሉ ህዝቡ እየደኸየ የሚሄድባት ሀገር መረጋጋትን ልታመጣ ትችል ይሆናል፤ ነገር ግን እድገትን አምጥታለች ወይ የሚለው አሁንም ምላሽ ያላገኘ ትልቅ ጥያቄ መሆኑን ጽሁፉ በፅኑ ያስገነዝባል።
2 days ago
ወደ ዘላቂ ልማት የሚደረግ ሽግግር
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 28፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ኢትዮጵያ ለመዋቅራዊ ሽግግር፣ ለኢኮኖሚ ጥንካሬ እና ለአካታች ሀገራዊ እድገት ቁርጠኝነት ባለው ሥርዓት እየተመራች በዘመናዊ ታሪክ ግንባታዋ ወሳኝ ምዕራፍ ላይ ትገኛለች።
በሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ ኢትዮጵያ በዋና ዋና ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ዘርፎች ላይ አበይት ስኬቶችን እያስመዘገበች ነው፡፡
የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ መሰረት የሆነው ግብርና ወደ ቴክኖሎጂ መር ያደረገው ሽግግር ተጨባጭ ውጤት እያስመዘገበ ይገኛል፡፡
በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት እና በክላስተር እርሻ እቅዶች አማካኝነት ኢትዮጵያ የሀገር ውስጥ ምርትን በከፍተኛ ሁኔታ አሳድጋለች፡፡ይህም ከውጭ የሚገቡ ምርቶች ጥገኝነትን ቀንሷል፡፡
በሀገሪቱ በአረንጓዴ ዐሻራ ፕሮግራሞች በአትክልትና ፍራፍሬ ላይ የተደረጉ ኢንቨስትመንቶች የአየር ንብረት ተፅዕኖን ለመቋቋም ሥነ ምህዳርን ለማከም እና የኑሮ ውድነትን ለማረጋጋት የሚደረገውን ጉዞ እየደገፈ ነው፡፡
የኃይል ማመንጨት አቅምን በማሳደግ የመንገድ መረቦችን በማዘመን እና በማስተሳሰር የኢትዮጵያ የመሰረተ ልማት ገጽታ አስደናቂ ለውጥ በማድረግ፤ የሀገር ውስጥ ትስስርን እያጠናከረ ኢትዮጵያን በአህጉራዊ ነጻ ንግድ ቀጣና ስር የንግድ ማዕከል እያደረጋት ይገኛል።
በአዲስ አበባ እና በክልል ከተሞች የተካሄደው የኮሪደር ልማት የሕዝብ ቦታዎችን በመሠረታዊነት በማደስ፤ መንገዶችን በማዘመን፣ አረንጓዴ የሕዝብ ቦታዎችን በመገንባት፣ የመገልገያ መሠረተ ልማቶችን በማስፋፋት እና የንፅህና አጠባበቅ ሥርዓቶችን በማሻሻል ተስማሚ የከተማ አካባቢን እየፈጠረ ነው፡፡
ዘላቂ ኢኮኖሚ ለመገንባት ኢትዮጵያ በዲጂታል ኢትዮጵያ ስትራቴጂ አማካኝነት የዲጂታል ሽግግርን በከፍተኛ ሁኔታ እያፋጠነች ትገኛለች።
በቴሌኮሙኒኬሽን እና በፋይናንስ ዘርፍ ላይ የተደረጉ ኢንቨስትመንቶች የፋይናንስ አካታችነትን እያሳደገ ነው፡፡
የኢንዱስትሪ ፓርኮችን ለማስፋፋት የሀገር ውስጥ ማኑፋክቸሪንግን ለማነቃቃት እና ከፍተኛ ዋጋ ያላቸውን የውጭ ኢንቨስትመንቶችን ለመሳብ የሚደረጉ ጥረቶች የኤክስፖርት ገቢን በማሳደግ የሰለጠነ የሰው ሀይል መፍጠራቸውን ቀጥለዋል።
የኢኮኖሚ እድገት ያለ ማህበራዊ ልማት ትርጉም የለውምና የኢትዮጵያ መንግሥት በትምህርት፣ ጤና እና ሌሎች ዘርፎች መሠረተ ልማቶችን በማሻሻል የሰራተኛውን ክህሎት ከዘመናዊ የገበያ ፍላጎት ጋር በማጣጣም የዜጎችን ሁለንተናዊ ለውጥ ማጠናከር ተችሏል።
ኢትዮጵያ እስካሁን ላስመዘገበቻቸው ስኬቶች በዓለም አቀፍ ደረጃ የተሰጧት እውቅናዎች የበለጸገች ሉዓላዊት ሀገር ለመገንባት በሚደረገው ጥረት ውስጥ ፈተናዎች ቢኖሩም ህዝብ ከውጤት ተኮር አመራር ጋር ተቀናጅቶ ወደ ዘላቂ ልማት የሚያደርገው ጉዞ በተገቢ መስመር ላይ ስለመሆኑ ማሳያ ናቸው።
በምሕረት ደምሴ
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 28፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ኢትዮጵያ ለመዋቅራዊ ሽግግር፣ ለኢኮኖሚ ጥንካሬ እና ለአካታች ሀገራዊ እድገት ቁርጠኝነት ባለው ሥርዓት እየተመራች በዘመናዊ ታሪክ ግንባታዋ ወሳኝ ምዕራፍ ላይ ትገኛለች።
በሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ ኢትዮጵያ በዋና ዋና ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ዘርፎች ላይ አበይት ስኬቶችን እያስመዘገበች ነው፡፡
የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ መሰረት የሆነው ግብርና ወደ ቴክኖሎጂ መር ያደረገው ሽግግር ተጨባጭ ውጤት እያስመዘገበ ይገኛል፡፡
በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት እና በክላስተር እርሻ እቅዶች አማካኝነት ኢትዮጵያ የሀገር ውስጥ ምርትን በከፍተኛ ሁኔታ አሳድጋለች፡፡ይህም ከውጭ የሚገቡ ምርቶች ጥገኝነትን ቀንሷል፡፡
በሀገሪቱ በአረንጓዴ ዐሻራ ፕሮግራሞች በአትክልትና ፍራፍሬ ላይ የተደረጉ ኢንቨስትመንቶች የአየር ንብረት ተፅዕኖን ለመቋቋም ሥነ ምህዳርን ለማከም እና የኑሮ ውድነትን ለማረጋጋት የሚደረገውን ጉዞ እየደገፈ ነው፡፡
የኃይል ማመንጨት አቅምን በማሳደግ የመንገድ መረቦችን በማዘመን እና በማስተሳሰር የኢትዮጵያ የመሰረተ ልማት ገጽታ አስደናቂ ለውጥ በማድረግ፤ የሀገር ውስጥ ትስስርን እያጠናከረ ኢትዮጵያን በአህጉራዊ ነጻ ንግድ ቀጣና ስር የንግድ ማዕከል እያደረጋት ይገኛል።
በአዲስ አበባ እና በክልል ከተሞች የተካሄደው የኮሪደር ልማት የሕዝብ ቦታዎችን በመሠረታዊነት በማደስ፤ መንገዶችን በማዘመን፣ አረንጓዴ የሕዝብ ቦታዎችን በመገንባት፣ የመገልገያ መሠረተ ልማቶችን በማስፋፋት እና የንፅህና አጠባበቅ ሥርዓቶችን በማሻሻል ተስማሚ የከተማ አካባቢን እየፈጠረ ነው፡፡
ዘላቂ ኢኮኖሚ ለመገንባት ኢትዮጵያ በዲጂታል ኢትዮጵያ ስትራቴጂ አማካኝነት የዲጂታል ሽግግርን በከፍተኛ ሁኔታ እያፋጠነች ትገኛለች።
በቴሌኮሙኒኬሽን እና በፋይናንስ ዘርፍ ላይ የተደረጉ ኢንቨስትመንቶች የፋይናንስ አካታችነትን እያሳደገ ነው፡፡
የኢንዱስትሪ ፓርኮችን ለማስፋፋት የሀገር ውስጥ ማኑፋክቸሪንግን ለማነቃቃት እና ከፍተኛ ዋጋ ያላቸውን የውጭ ኢንቨስትመንቶችን ለመሳብ የሚደረጉ ጥረቶች የኤክስፖርት ገቢን በማሳደግ የሰለጠነ የሰው ሀይል መፍጠራቸውን ቀጥለዋል።
የኢኮኖሚ እድገት ያለ ማህበራዊ ልማት ትርጉም የለውምና የኢትዮጵያ መንግሥት በትምህርት፣ ጤና እና ሌሎች ዘርፎች መሠረተ ልማቶችን በማሻሻል የሰራተኛውን ክህሎት ከዘመናዊ የገበያ ፍላጎት ጋር በማጣጣም የዜጎችን ሁለንተናዊ ለውጥ ማጠናከር ተችሏል።
ኢትዮጵያ እስካሁን ላስመዘገበቻቸው ስኬቶች በዓለም አቀፍ ደረጃ የተሰጧት እውቅናዎች የበለጸገች ሉዓላዊት ሀገር ለመገንባት በሚደረገው ጥረት ውስጥ ፈተናዎች ቢኖሩም ህዝብ ከውጤት ተኮር አመራር ጋር ተቀናጅቶ ወደ ዘላቂ ልማት የሚያደርገው ጉዞ በተገቢ መስመር ላይ ስለመሆኑ ማሳያ ናቸው።
በምሕረት ደምሴ
2 days ago
የ112 ፍልስጤማውያን የቀብር ስነ ስርዓት በዛሬው እለት አንድ ላይ ተፈጸመ
#ethiopia | በ2023 በእስራኤል ወታደራዊ ጥቃት ህይወታቸውን ያጡ በወቅቱ አስከሬናቸው ያልተመለሰ 112 ዜጎች ስርአተ ቀብራቸው ዛሬ ተፈፅሟል።
112 የፍልስጤማዊያን አስከሬኖች በቅርቡ በተደረገው ስምምነት መሰረት እስራኤል የመለሰች ሲሆን አብዛኞቹ አስከሬኖች ማንነታቸው በውል አይታወቅም ተብሏል።
አስክሬኖቹ ማንነታቸው ለማወቅ ባለመቻሉ እና ሙሉ በሙሉ መለየት ሳይቻል የቀሩ በመሆናቸው በጋዛ በይፋ በጋራ እንዲያርፉ ተደርጓል ሲል አልጀዚራ ፅፏል።
ከዚህ በተጨማሪም አስከሬኖቹ በእስራኤል ጦር ተይዘው ከቆዩ በኋላ የተመለሱ ቢሆንም የበርካቶቹ ማንነት ሳይለይ በመቅረቱ በቁጥር እና በመለያ ምልክቶች ብቻ ተመዝግበው እንዲያርፉ ተደርጓል ብሏል።
በሺዎች የሚቆጠሩ የጋዛ ነዋሪዎች እና የሟች ቤተሰቦች በቀብር ስነ ስርዓቱ ላይ ተገኝተዋል።
የሰብአዊ መብት ተሟጋቾችም የሟቾችን አስከሬን ይዞ ማቆየት ህገ ወጥ መሆኑን በመግለጽ ድርጊቱን ኮንነውታል።
የጋዛ የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር እንዳስታወቀው አሁንም በሺዎች የሚቆጠሩ የፍልስጤማውያን አስከሬን በፍርስራሾች ስር እንደሚገኝ ገልጿል።
ሔኖክ ወ/ገብርኤል
#ethiopia #getutemesgen #getunews #gaza #massfuneral #sabraattack
#ethiopia | በ2023 በእስራኤል ወታደራዊ ጥቃት ህይወታቸውን ያጡ በወቅቱ አስከሬናቸው ያልተመለሰ 112 ዜጎች ስርአተ ቀብራቸው ዛሬ ተፈፅሟል።
112 የፍልስጤማዊያን አስከሬኖች በቅርቡ በተደረገው ስምምነት መሰረት እስራኤል የመለሰች ሲሆን አብዛኞቹ አስከሬኖች ማንነታቸው በውል አይታወቅም ተብሏል።
አስክሬኖቹ ማንነታቸው ለማወቅ ባለመቻሉ እና ሙሉ በሙሉ መለየት ሳይቻል የቀሩ በመሆናቸው በጋዛ በይፋ በጋራ እንዲያርፉ ተደርጓል ሲል አልጀዚራ ፅፏል።
ከዚህ በተጨማሪም አስከሬኖቹ በእስራኤል ጦር ተይዘው ከቆዩ በኋላ የተመለሱ ቢሆንም የበርካቶቹ ማንነት ሳይለይ በመቅረቱ በቁጥር እና በመለያ ምልክቶች ብቻ ተመዝግበው እንዲያርፉ ተደርጓል ብሏል።
በሺዎች የሚቆጠሩ የጋዛ ነዋሪዎች እና የሟች ቤተሰቦች በቀብር ስነ ስርዓቱ ላይ ተገኝተዋል።
የሰብአዊ መብት ተሟጋቾችም የሟቾችን አስከሬን ይዞ ማቆየት ህገ ወጥ መሆኑን በመግለጽ ድርጊቱን ኮንነውታል።
የጋዛ የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር እንዳስታወቀው አሁንም በሺዎች የሚቆጠሩ የፍልስጤማውያን አስከሬን በፍርስራሾች ስር እንደሚገኝ ገልጿል።
ሔኖክ ወ/ገብርኤል
#ethiopia #getutemesgen #getunews #gaza #massfuneral #sabraattack
2 days ago
ይህን እሽግ እንደተራ መክሰስ ለገበያ ማቅረብ ወንጀል ነው!
#ethiopia | በከባድ የምግብ እጥረት የተጎዱ ሕፃናትን ሕይወት ለማዳን የሚሰጠው አጣዳፊ የምግብ መድኃኒት (RUTF) ወይ በተለምዶ ስሙ ፕላምፕሌት በገበያ ላይ ለንግድ መቅረቡና ለክብደት መጨመሪያ መዋሉ ከፍተኛ የሞራልና የሕግ ተጠያቂነትን የሚያስከትል ወንጀል መሆኑ ተገለጸ።
በሞት አፋፍ ላይ የሚገኙ ሕፃናትን ለማዳን በልዩ ሁኔታ የተዘጋጀውን ይህን ሕይወት አድን እሽግ እንደ ተራ መክሰስ ለገበያ ማቅረብ በእርግጥም ህክምናው ለሚገባቸው ሕፃናት የሚደርሰውን እርዳታ በመንጠቅ ሕይወታቸውን ለሞት አደጋ የሚያጋልጥ ተግባር ነው።
በሌላ በኩል ይህ ምርት በካሎሪ፣ በቅባትና በቫይታሚኖች እጅግ የበለፀገ በመሆኑ ጤናማ ሰዎች ሳያስፈልጋቸው ሲመገቡት ለከፍተኛ የኩላሊትና የጉበት ጫና፣ ለደም ስኳርና ቅባት መዛባት እንዲሁም ለቫይታሚን መርዝነት ያጋልጣቸዋል።
በመሆኑም በነፃ ወይም በሕክምና ተቋማት በኩል ለተቸገሩ ሕፃናት የተላከን እርዳታ መሸጥም ሆነ መግዛት በሕግ የሚያስጠይቅ ወንጀል በመሆኑ፣ ሕይወት አድን መድኃኒቶች የንግድ ዕቃ አለመሆናቸውን ተረድቶ ኅብረተሰቡ ከዚህ ድርጊት ሊቆጠብ እንደሚገባ መልእክት ተላልፏል።
(via ጤና)
በያፌት ገ/ህይወት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#ethiopia | በከባድ የምግብ እጥረት የተጎዱ ሕፃናትን ሕይወት ለማዳን የሚሰጠው አጣዳፊ የምግብ መድኃኒት (RUTF) ወይ በተለምዶ ስሙ ፕላምፕሌት በገበያ ላይ ለንግድ መቅረቡና ለክብደት መጨመሪያ መዋሉ ከፍተኛ የሞራልና የሕግ ተጠያቂነትን የሚያስከትል ወንጀል መሆኑ ተገለጸ።
በሞት አፋፍ ላይ የሚገኙ ሕፃናትን ለማዳን በልዩ ሁኔታ የተዘጋጀውን ይህን ሕይወት አድን እሽግ እንደ ተራ መክሰስ ለገበያ ማቅረብ በእርግጥም ህክምናው ለሚገባቸው ሕፃናት የሚደርሰውን እርዳታ በመንጠቅ ሕይወታቸውን ለሞት አደጋ የሚያጋልጥ ተግባር ነው።
በሌላ በኩል ይህ ምርት በካሎሪ፣ በቅባትና በቫይታሚኖች እጅግ የበለፀገ በመሆኑ ጤናማ ሰዎች ሳያስፈልጋቸው ሲመገቡት ለከፍተኛ የኩላሊትና የጉበት ጫና፣ ለደም ስኳርና ቅባት መዛባት እንዲሁም ለቫይታሚን መርዝነት ያጋልጣቸዋል።
በመሆኑም በነፃ ወይም በሕክምና ተቋማት በኩል ለተቸገሩ ሕፃናት የተላከን እርዳታ መሸጥም ሆነ መግዛት በሕግ የሚያስጠይቅ ወንጀል በመሆኑ፣ ሕይወት አድን መድኃኒቶች የንግድ ዕቃ አለመሆናቸውን ተረድቶ ኅብረተሰቡ ከዚህ ድርጊት ሊቆጠብ እንደሚገባ መልእክት ተላልፏል።
(via ጤና)
በያፌት ገ/ህይወት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
2 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የሱማሊላንድ ፕሬዝደንት የኩላሊት ዲያሊሲስ አገልግሎት በነፃ እንዲሰጥ ትእዛዝ ሰጡ፡፡ የሱማሊላንድ ፕሬዝደንት አብዱራህማን መሀመድ ኢሮ በአገራቸው ውስጥ በነፃ የኩላሊት ዲያሊሲስ አገልግሎት እንዲሰጥ ትእዛዝ ማስተላፋቸውን ሂራን ኒውስ ዘገበ፡፡
እንደዘገባው ይህንን ትእዛዝ ለመስጠት የተገደዱት ህሙማን በቂ አገልግሎት ባለመኖሩ ለከፍተኛ ወጪ እየተዳረጉ መሆናቸውን በመግለፃቸው ነው፡፡ ትላንት ከሱማሊላንድ ፕሬዝደንት ፅህፈት ቤት የወጣው መመሪያ የአገሪቱ ጤና ሚኒስትር በአስቸኳይ 12 የዲያሊሲስ ማሽኖችን እንዲገዛና በሀርጌሳ አጠቃላይ ሆስፒታል የሚሰጠውን ይህንን ህክምና እንዲያሰፋ ትእዛዝ ማስተላለፉን ዘገባው አስረድቷል፡፡ ይህ የፕሬዝደንቱ መመሪያ ማንኛውም የኩላሊት ህመም ህክምና ዲያሊሲስን ጨምሮ በነፃ እንዲሰጥም የሚገልፅ ነው፡፡
ፕሬዝደንቱ ይህንን መመሪያ ከመስጠታቸው ከጥቂት ቀናት በፊት በሀርጌሳ አጠቃላይ ሆስፒታል ተገኝተው ጉብኝት በማድረግ ከህሙማን፣ ከአስተዳደሩና ከዶክተሮች ጋር ውይይት አድርገው ነበር፡፡ ለዚህ ጉብኝት መሰረት የሆናቸው ደግሞ ባለፈው ሳምንት በርካታ የኩላሊት ህሙማን በሆስፒታሉ ግቢ ውስጥ የተቃውሞ ሰልፍ ማድረጋቸው እንደሆነ ከዘገባው ላይ ተመልክተናል፡፡
እንደዘገባው ይህንን ትእዛዝ ለመስጠት የተገደዱት ህሙማን በቂ አገልግሎት ባለመኖሩ ለከፍተኛ ወጪ እየተዳረጉ መሆናቸውን በመግለፃቸው ነው፡፡ ትላንት ከሱማሊላንድ ፕሬዝደንት ፅህፈት ቤት የወጣው መመሪያ የአገሪቱ ጤና ሚኒስትር በአስቸኳይ 12 የዲያሊሲስ ማሽኖችን እንዲገዛና በሀርጌሳ አጠቃላይ ሆስፒታል የሚሰጠውን ይህንን ህክምና እንዲያሰፋ ትእዛዝ ማስተላለፉን ዘገባው አስረድቷል፡፡ ይህ የፕሬዝደንቱ መመሪያ ማንኛውም የኩላሊት ህመም ህክምና ዲያሊሲስን ጨምሮ በነፃ እንዲሰጥም የሚገልፅ ነው፡፡
ፕሬዝደንቱ ይህንን መመሪያ ከመስጠታቸው ከጥቂት ቀናት በፊት በሀርጌሳ አጠቃላይ ሆስፒታል ተገኝተው ጉብኝት በማድረግ ከህሙማን፣ ከአስተዳደሩና ከዶክተሮች ጋር ውይይት አድርገው ነበር፡፡ ለዚህ ጉብኝት መሰረት የሆናቸው ደግሞ ባለፈው ሳምንት በርካታ የኩላሊት ህሙማን በሆስፒታሉ ግቢ ውስጥ የተቃውሞ ሰልፍ ማድረጋቸው እንደሆነ ከዘገባው ላይ ተመልክተናል፡፡
2 days ago
ብሩስ ዊሊስ ባለቤት የባለቤቷን ህመም (FTD) ለመከታተል የሚያስችል ህግ እንዲፀድቅ ግፊት አደረገች
የታዋቂው የፊልም ኮከብ ብሩስ ዊሊስ ባለቤት የሆነችው ኤማ ሄሚንግ ዊሊስ፣ ባለቤቷ የተጠቃበትን 'የፊት ለፊት የጭንቅላት ክፍል መጎዳት' (Frontotemporal Degeneration - FTD) የተሰኘውን የመርሳት ህመም የሚከታተል ህግ እንዲፀድቅ ሰኞ ዕለት በካሊፎርኒያ ካፒቶል ከሚገኙ ህግ አውጪዎች ጋር በመሆን ግፊት አድርጋለች።
በሴናተር ሮጀር ኒየሎ የተዘጋጀው እና ኤማ ሄሚንግ ዊሊስ ድጋፏን የሰጠችለት ይህ ረቂቅ ህግ፣ የካሊፎርኒያ የህዝብ ጤና መምሪያ ስለ FTD ህመም መረጃዎችን እንዲሰበስብ የሚያስገድድ ነው። መምሪያው በአሁኑ ወቅት የሃንቲንግተን፣ የፓርኪንሰንስ፣ የአልዛይመርስ እና የማልቲፕል ስክለሮሲስ በሽታዎችን መረጃዎች በመሰብሰብ ላይ ይገኛል። የህጉን ሂደት በተመለከተ፣ ረቂቅ ህጉ ሀምሌ 1 ቀን የህግ አውጪው ምክር ቤት የአንድ ወር የክረምት እረፍት ከመውጣቱ በፊት በምክር ቤቱ ተጠባባቂ መዝገብ ውስጥ ሰፍሮ ነበር። ምክር ቤቱ ሰኞ ዕለት ስራውን የጀመረ ሲሆን፣ ረቂቅ ህጎችን ለማጽደቅ የአንድ ወር ጊዜ ብቻ ቀርቶታል። ይህ የህግ ማዕቀፍ እስከ ጥር 1፣ 2032 ድረስ የሚራዘም ሲሆን፣ የህጉ ትንታኔ እንደሚያሳየው ለሰራተኞች እና ለኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ክፍያን ጨምሮ በዓመት 2.7 ሚሊዮን ዶላር በጀት ይጠይቃል።
ኤማ ሰኞ ዕለት በካፒቶል በሰጠችው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ እንዳብራራችው፣ FTDን በነርቭ መጎዳት በሽታዎች መዝገብ ውስጥ ማካተት የካሊፎርኒያ ታካሚዎችን መቁጠር ብቻ ሳይሆን፣ በካሊፎርኒያ የሚገኙ የባዮቴክ ተመራማሪዎች ህክምና እና ፈውስ ለማግኘት የሚፈልጉትን ጠቃሚ የመረጃ ቋት መገንባት ነው። ባለቤቷ ለመጀመሪያ ጊዜ በ2022 በበሽታው መያዙ እንደታወቀ የጠቀሰችው ኤማ፣ አሁን ላይ ህመሙን የሚያዘገይ ወይም የሚያቆም ህክምና እንደሌለ ብታምንም፣ የህመሙን መረጃዎች መሰብሰብ ግን ለምርምር ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳለው ተናግራለች። ታዋቂው ተዋናይ ስለሚገኝበት ሁኔታ ተጠይቃ ስትመልስም፣ በዚህ እጅግ ጨካኝ በሆነ በሽታ ውስጥ ሆኖ ማድረግ የሚችለውን ያህል በጥሩ ሁኔታ ላይ ይገኛል ብዬ አስባለሁ ስትል ገልጻለች።
'ፒክስ ዲዚዝ' በመባልም የሚታወቀው ይህ ህመም፣ ከግንባር ጀርባ ወይም ከጆሮ አካባቢ ባሉ የጭንቅላት ክፍሎች ላይ በሚከሰት የነርቭ ሴሎች መጎዳት የሚመጣ የጭንቅላት እክል ነው። የበሽታው ምልክቶች የባህሪ እና የስብዕና ለውጥን፣ ስሜት አልባ መሆንን ፣ ውሳኔ የመስጠት፣ የመንቀሳቀስ እና የመናገር ችግርን፣ እንዲሁም ቃላትን የመረዳት አቅም ማጣትን ያካትታሉ።
የኤፍ ቲ ዲ ማህበር የጥብቅና እና የበጎ ፈቃደኞች ተሳትፎ ዳይሬክተር የሆኑት ሜጋን ቡዝቢ እንደገለጹት፣ የታካሚ ቤተሰቦች እነዚህ ምልክቶች ሲታዩ ከሐኪሞች ግልጽ የሆነ ምላሽ ለማግኘት ብዙ ጊዜ ይቸገራሉ። ዳይሬክተሯ አክለውም፣ ይህ ሁኔታ ለብዙ የካሊፎርኒያ ቤተሰቦች የFTD ምርመራ ውጤትን ለማግኘት የሚያደርጉት ረጅም እና አድካሚ ጉዞ እውነታ መሆኑን አብራርተዋል። በአሁኑ ወቅት በሽታውን ለማከም የሚረዱ ህክምናዎች እጅግ ውስን ሲሆኑ፣ ፈውስም እስካሁን አልተገኘለትም።
የታዋቂው የፊልም ኮከብ ብሩስ ዊሊስ ባለቤት የሆነችው ኤማ ሄሚንግ ዊሊስ፣ ባለቤቷ የተጠቃበትን 'የፊት ለፊት የጭንቅላት ክፍል መጎዳት' (Frontotemporal Degeneration - FTD) የተሰኘውን የመርሳት ህመም የሚከታተል ህግ እንዲፀድቅ ሰኞ ዕለት በካሊፎርኒያ ካፒቶል ከሚገኙ ህግ አውጪዎች ጋር በመሆን ግፊት አድርጋለች።
በሴናተር ሮጀር ኒየሎ የተዘጋጀው እና ኤማ ሄሚንግ ዊሊስ ድጋፏን የሰጠችለት ይህ ረቂቅ ህግ፣ የካሊፎርኒያ የህዝብ ጤና መምሪያ ስለ FTD ህመም መረጃዎችን እንዲሰበስብ የሚያስገድድ ነው። መምሪያው በአሁኑ ወቅት የሃንቲንግተን፣ የፓርኪንሰንስ፣ የአልዛይመርስ እና የማልቲፕል ስክለሮሲስ በሽታዎችን መረጃዎች በመሰብሰብ ላይ ይገኛል። የህጉን ሂደት በተመለከተ፣ ረቂቅ ህጉ ሀምሌ 1 ቀን የህግ አውጪው ምክር ቤት የአንድ ወር የክረምት እረፍት ከመውጣቱ በፊት በምክር ቤቱ ተጠባባቂ መዝገብ ውስጥ ሰፍሮ ነበር። ምክር ቤቱ ሰኞ ዕለት ስራውን የጀመረ ሲሆን፣ ረቂቅ ህጎችን ለማጽደቅ የአንድ ወር ጊዜ ብቻ ቀርቶታል። ይህ የህግ ማዕቀፍ እስከ ጥር 1፣ 2032 ድረስ የሚራዘም ሲሆን፣ የህጉ ትንታኔ እንደሚያሳየው ለሰራተኞች እና ለኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ክፍያን ጨምሮ በዓመት 2.7 ሚሊዮን ዶላር በጀት ይጠይቃል።
ኤማ ሰኞ ዕለት በካፒቶል በሰጠችው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ እንዳብራራችው፣ FTDን በነርቭ መጎዳት በሽታዎች መዝገብ ውስጥ ማካተት የካሊፎርኒያ ታካሚዎችን መቁጠር ብቻ ሳይሆን፣ በካሊፎርኒያ የሚገኙ የባዮቴክ ተመራማሪዎች ህክምና እና ፈውስ ለማግኘት የሚፈልጉትን ጠቃሚ የመረጃ ቋት መገንባት ነው። ባለቤቷ ለመጀመሪያ ጊዜ በ2022 በበሽታው መያዙ እንደታወቀ የጠቀሰችው ኤማ፣ አሁን ላይ ህመሙን የሚያዘገይ ወይም የሚያቆም ህክምና እንደሌለ ብታምንም፣ የህመሙን መረጃዎች መሰብሰብ ግን ለምርምር ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳለው ተናግራለች። ታዋቂው ተዋናይ ስለሚገኝበት ሁኔታ ተጠይቃ ስትመልስም፣ በዚህ እጅግ ጨካኝ በሆነ በሽታ ውስጥ ሆኖ ማድረግ የሚችለውን ያህል በጥሩ ሁኔታ ላይ ይገኛል ብዬ አስባለሁ ስትል ገልጻለች።
'ፒክስ ዲዚዝ' በመባልም የሚታወቀው ይህ ህመም፣ ከግንባር ጀርባ ወይም ከጆሮ አካባቢ ባሉ የጭንቅላት ክፍሎች ላይ በሚከሰት የነርቭ ሴሎች መጎዳት የሚመጣ የጭንቅላት እክል ነው። የበሽታው ምልክቶች የባህሪ እና የስብዕና ለውጥን፣ ስሜት አልባ መሆንን ፣ ውሳኔ የመስጠት፣ የመንቀሳቀስ እና የመናገር ችግርን፣ እንዲሁም ቃላትን የመረዳት አቅም ማጣትን ያካትታሉ።
የኤፍ ቲ ዲ ማህበር የጥብቅና እና የበጎ ፈቃደኞች ተሳትፎ ዳይሬክተር የሆኑት ሜጋን ቡዝቢ እንደገለጹት፣ የታካሚ ቤተሰቦች እነዚህ ምልክቶች ሲታዩ ከሐኪሞች ግልጽ የሆነ ምላሽ ለማግኘት ብዙ ጊዜ ይቸገራሉ። ዳይሬክተሯ አክለውም፣ ይህ ሁኔታ ለብዙ የካሊፎርኒያ ቤተሰቦች የFTD ምርመራ ውጤትን ለማግኘት የሚያደርጉት ረጅም እና አድካሚ ጉዞ እውነታ መሆኑን አብራርተዋል። በአሁኑ ወቅት በሽታውን ለማከም የሚረዱ ህክምናዎች እጅግ ውስን ሲሆኑ፣ ፈውስም እስካሁን አልተገኘለትም።
Sponsored by
Surafel
2 days ago
የጋዜጠኛና መምህር ዐቢይ ይልማ 5ኛ መጽሐፍ
“ደህና ነኝ – እግዚአብሔር ይመስገን” ቅዳሜ ይመረቃል
#ethiopia | የጋዜጠኛ፣ ደራሲና መምህር ዐቢይ ይልማ አምስተኛ መጽሐፍ የሆነው “ደህና ነኝ – እግዚአብሔር ይመስገን” ቅዳሜ ነሐሴ 2፣ 2018 ዓ.ም. ከጠዋቱ 4፡00 ጀምሮ በቦሌ በሚገኘው ዓለም ሲኒማ ይመረቃል።
መጽሐፉ በዘመናችን በብዙ ሰዎች የሚስተዋሉ እንደ ጭንቀት፣ ፍርሃት፣ የባዶነት ስሜት፣ ተስፋ መቁረጥ፣ ሱሰኝነት፣ የገንዘብ ችግርና ሌሎች የሕይወት ፈተናዎች ዙሪያ መንፈሳዊና ሳይንሳዊ እይታዎችን በማቀናጀት ለአንባቢያን ተስፋና መነሳሳት ለመስጠት ያለመ ሥራ መሆኑን አዘጋጆቹ ገልጸዋል።
ደራሲው ዐቢይ ይልማ በሕይወቱ ያጋጠሙትን ለ12 ዓመታት የዘለቀ ከባድ የጤናና የሕይወት ፈተና በድል ካለፉ በኋላ ያገኙትን ልምድና እውቀት በዚህ መጽሐፍ አካፍለዋል።
አዘጋጅ ኮሚቴው በዕለቱ የሚካሄደውን የመጽሐፍ ምረቃ ሥነ ሥርዓት እንዲታደሙ የደራሲውን ወዳጆች፣ የሥነ ጽሑፍ አፍቃሪዎችና መላውን ሕዝብ በክብር ጋብዟል።
ቅዳሜ ነሐሴ 2፣ 2018 ዓ.ም.
ጠዋት 4፡00 ሰዓት
ቦሌ ዓለም ሲኒማ
እንኳን ወደ መጽሐፉ ምረቃ በደህና መጡ!
“ደህና ነኝ – እግዚአብሔር ይመስገን” ቅዳሜ ይመረቃል
#ethiopia | የጋዜጠኛ፣ ደራሲና መምህር ዐቢይ ይልማ አምስተኛ መጽሐፍ የሆነው “ደህና ነኝ – እግዚአብሔር ይመስገን” ቅዳሜ ነሐሴ 2፣ 2018 ዓ.ም. ከጠዋቱ 4፡00 ጀምሮ በቦሌ በሚገኘው ዓለም ሲኒማ ይመረቃል።
መጽሐፉ በዘመናችን በብዙ ሰዎች የሚስተዋሉ እንደ ጭንቀት፣ ፍርሃት፣ የባዶነት ስሜት፣ ተስፋ መቁረጥ፣ ሱሰኝነት፣ የገንዘብ ችግርና ሌሎች የሕይወት ፈተናዎች ዙሪያ መንፈሳዊና ሳይንሳዊ እይታዎችን በማቀናጀት ለአንባቢያን ተስፋና መነሳሳት ለመስጠት ያለመ ሥራ መሆኑን አዘጋጆቹ ገልጸዋል።
ደራሲው ዐቢይ ይልማ በሕይወቱ ያጋጠሙትን ለ12 ዓመታት የዘለቀ ከባድ የጤናና የሕይወት ፈተና በድል ካለፉ በኋላ ያገኙትን ልምድና እውቀት በዚህ መጽሐፍ አካፍለዋል።
አዘጋጅ ኮሚቴው በዕለቱ የሚካሄደውን የመጽሐፍ ምረቃ ሥነ ሥርዓት እንዲታደሙ የደራሲውን ወዳጆች፣ የሥነ ጽሑፍ አፍቃሪዎችና መላውን ሕዝብ በክብር ጋብዟል።
ቅዳሜ ነሐሴ 2፣ 2018 ዓ.ም.
ጠዋት 4፡00 ሰዓት
ቦሌ ዓለም ሲኒማ
እንኳን ወደ መጽሐፉ ምረቃ በደህና መጡ!
3 days ago
አሳዛኝ ታሪክ- የፔቲዲን ሱስ
#ethiopia | ዶክተር ካሳ አደጋ ያጋጥመውና የእጁ አጥንት ይሰበራል። ወደ ድንገተኛ ክፍል ሲሄድ ለህመም ማስታገሻ ፔቲዲን የተባለውን መርፌ ይወጉታል። የስብራቱ ህመም ይጠፋና የደስታ ስሜት ይሰማዋል። ከስብራቱ ቢያገግምም ለህመም ማስታገሻ የወሰደው ፔቲዲን ሱስ ሆኖበት በየቀኑ ብዙ ብልቃጦች ራሱን ይወጋል።
ፔቲዲን የሚፃፈው በልዩ የመድሀኒት ማዘዣ ነው። ዶክተር ካሳ ጓደኞቹ እንዲፅፉለት ይጠይቃቸዋል። መጀመሪያ ላይ ይፅፉለት ነበር። በኋላ ግን የሚወስደው መጠን ከፍ ስላለ "አንፅፍም!" ብለው ከለከሉት። አንዳንድ ባልደረቦቹ ግን እያዘኑለት ይፅፉለታል። የሚወስደው መድሀኒት መጠን ከፍ ሲል ልዩ የመድሀኒት ማዘዣውን ይዞ እራሱ እየፃፈ መግዛት ጀመረ። መድሀኒቱ ውድ ስለሆነ ዶክተር ካሳ አብዛኛው ደሞዙን በመድሀኒት ግዢ ነው የሚያጠፋው። ከባልደረቦቹም በተለያየ ጊዜ ብሮች ተበድሯል።
ዶክተር ካሳ ሱሱን ለማቆም ሞክሮ ያውቃል። ነገር ግን ሳይወስድ ሲቀር ላብበላብ ይሆናል። ተረጋግቶ መስራት አይችልም። ይቅበጠበጣል። መድሀኒቱን ባለመውሰዱ የሚሰማውን ምቾት የሚነሳ ስሜት ለማጥፋት ውሳኔውን ሽሮ ፔቲዲን ይወጋል።
አንድ ቀን ዶክተር ካሳ ሆስፒታሉ የሰጠው ቤት ውስጥ ራሱን ስቶ ተዘርሮ ወድቋል። ክፍሉ ውስጥ የፔቲዲን ብልቃጦች አሉ። መርፌና ሲሪንጅ አጠገቡ አለ....
ዶክተር ካሳ ልቦለዳዊ ስም ይሆን እንጂ ተመሳሳይ የፔቲዲን ሱስ ውስጥ ያሉ ብዙ ሰዎች አሉ። አብዛኞቹ ደግሞ የጤና ባለሞያዎች ናቸው። ነርሶች፣ የሰመመን ባለሞያዎች፣ ሀኪሞች፣ የፋርማሲ ባለምያዎች...። ህክምና ሞያ ውስጥ ጥቂት አመታት ያሳለፍን ሰዎች በዚህ ሱስ የሚቸገር የምናውቀው ሰው ወይም ወዳጅ አለን።
በሱስ የሚቸገሩ ሰዎች ላይ ፍረጃ ከማድረግ ይልቅ ሞያዊ እገዛ እንዲያገኙ ብናደርግ ጥሩ ያልሆኑ ነገሮች እንዳይከሰቱ ማድረግ እንችላለን። ሱስ ህክምና ያለው የአእምሮ ህመም ነው።
እኔ የምወደውን ሰው በፔቲዲን ሱስ ምክኒያት አጥቻለሁ። ይመለከተኛል። ሌሎች ሰዎች ተመሳሳይ ነገር ውስጥ እንዳያልፉና ተገቢውን የአእምሮ ህክምና እንዲያገኙ የምችለውን ያህል ግንዛቤ ለመፍጠር እጥራለሁ።
ያለ አእምሮ ጤና፤ ጤና የለም!
ዶ/ር ዮናስ ላቀው
#ethiopia | ዶክተር ካሳ አደጋ ያጋጥመውና የእጁ አጥንት ይሰበራል። ወደ ድንገተኛ ክፍል ሲሄድ ለህመም ማስታገሻ ፔቲዲን የተባለውን መርፌ ይወጉታል። የስብራቱ ህመም ይጠፋና የደስታ ስሜት ይሰማዋል። ከስብራቱ ቢያገግምም ለህመም ማስታገሻ የወሰደው ፔቲዲን ሱስ ሆኖበት በየቀኑ ብዙ ብልቃጦች ራሱን ይወጋል።
ፔቲዲን የሚፃፈው በልዩ የመድሀኒት ማዘዣ ነው። ዶክተር ካሳ ጓደኞቹ እንዲፅፉለት ይጠይቃቸዋል። መጀመሪያ ላይ ይፅፉለት ነበር። በኋላ ግን የሚወስደው መጠን ከፍ ስላለ "አንፅፍም!" ብለው ከለከሉት። አንዳንድ ባልደረቦቹ ግን እያዘኑለት ይፅፉለታል። የሚወስደው መድሀኒት መጠን ከፍ ሲል ልዩ የመድሀኒት ማዘዣውን ይዞ እራሱ እየፃፈ መግዛት ጀመረ። መድሀኒቱ ውድ ስለሆነ ዶክተር ካሳ አብዛኛው ደሞዙን በመድሀኒት ግዢ ነው የሚያጠፋው። ከባልደረቦቹም በተለያየ ጊዜ ብሮች ተበድሯል።
ዶክተር ካሳ ሱሱን ለማቆም ሞክሮ ያውቃል። ነገር ግን ሳይወስድ ሲቀር ላብበላብ ይሆናል። ተረጋግቶ መስራት አይችልም። ይቅበጠበጣል። መድሀኒቱን ባለመውሰዱ የሚሰማውን ምቾት የሚነሳ ስሜት ለማጥፋት ውሳኔውን ሽሮ ፔቲዲን ይወጋል።
አንድ ቀን ዶክተር ካሳ ሆስፒታሉ የሰጠው ቤት ውስጥ ራሱን ስቶ ተዘርሮ ወድቋል። ክፍሉ ውስጥ የፔቲዲን ብልቃጦች አሉ። መርፌና ሲሪንጅ አጠገቡ አለ....
ዶክተር ካሳ ልቦለዳዊ ስም ይሆን እንጂ ተመሳሳይ የፔቲዲን ሱስ ውስጥ ያሉ ብዙ ሰዎች አሉ። አብዛኞቹ ደግሞ የጤና ባለሞያዎች ናቸው። ነርሶች፣ የሰመመን ባለሞያዎች፣ ሀኪሞች፣ የፋርማሲ ባለምያዎች...። ህክምና ሞያ ውስጥ ጥቂት አመታት ያሳለፍን ሰዎች በዚህ ሱስ የሚቸገር የምናውቀው ሰው ወይም ወዳጅ አለን።
በሱስ የሚቸገሩ ሰዎች ላይ ፍረጃ ከማድረግ ይልቅ ሞያዊ እገዛ እንዲያገኙ ብናደርግ ጥሩ ያልሆኑ ነገሮች እንዳይከሰቱ ማድረግ እንችላለን። ሱስ ህክምና ያለው የአእምሮ ህመም ነው።
እኔ የምወደውን ሰው በፔቲዲን ሱስ ምክኒያት አጥቻለሁ። ይመለከተኛል። ሌሎች ሰዎች ተመሳሳይ ነገር ውስጥ እንዳያልፉና ተገቢውን የአእምሮ ህክምና እንዲያገኙ የምችለውን ያህል ግንዛቤ ለመፍጠር እጥራለሁ።
ያለ አእምሮ ጤና፤ ጤና የለም!
ዶ/ር ዮናስ ላቀው
3 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና ዳሰሳ) በኢትዮጵያ እና በአሜሪካ መንግስት መካከል የተፈረመው የ1.616 ቢሊዮን ዶላር የሕዝብ ጤና ትብብር ስምምነት፣ የሀገሪቱን የፖሊሲ ነፃነት፣ ግልፅነት እና እውነተኛ አፈፃፀም አስመልክቶ አዳዲስ ሂሳዊ ጥያቄዎችን ማስነሳቱን አንድ አዲስ ጥናት ይፋ አደረገ። በእንግሊዙ ብሪስቶል ዩኒቨርሲቲ በጤና ኢኮኖሚክስ እና ፖሊሲ ትንተና ባለሙያ የቀረበው ይህ ጥናት፣ ስምምነቱ የሀገሪቱን የጤና ዘርፍ ያጠናክራል ተብሎ ቢነገርለትም፣ ከጎረቤት ሀገራት ተሞክሮ እና ከሀገር ውስጥ ነባራዊ ሁኔታ አኳያ በርካታ የትኩረት ክፍተቶች እንዳሉበት አመልክቷል።
የስምምነቱ ዝርዝር እና የኬንያ ንፅፅር
በታህሳስ 2018 (ዲሴምበር 2025) በጤና ሚኒስትሯ ዶ/ር መቅደስ ዳባ፣ በፋይናንስ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ እና በአሜሪካው አምባሳደር ኤርቪን ማሲንጋ መካከል የተፈረመው ይህ ስምምነት፣ አሜሪካ እስከ 1.166 ቢሊዮን ዶላር (ተጨማሪ የብቃት ድጋፍን ጨምሮ) እና ኢትዮጵያ 450 ሚሊዮን ዶላር በሀገር ውስጥ የሚሸፍኑበት ነው። ነገር ግን ጥናቱ እንደሚያሳየው፣ አጠቃላይ የህዝብ ብዛቷ የኢትዮጵያን ግማሽ ያህል የምትሆነው ጎረቤት ሀገር ኬንያ፣ በተመሳሳይ ጊዜ ከዩናይትድ ስቴትስ ጋር የ2.5 ቢሊዮን ዶላር ስምምነት ተፈራርማለች።
የኢትዮጵያ የህዝብ ብዛት እጅግ የበዛ ሆኖ እያለ፣ ለምን ከኬንያ በእጅጉ ያነሰ የፋይናንስ ድጋፍ ለመቀበል ተስማማች የሚለው ጥያቄ የሙያተኞችን ትኩረት ስቧል። የኢትዮጵያ ተደራዳሪዎች ከህዝብ ብዛታቸው አኳያ ከኬንያ እጥፍ ወይም እስከ 5 ቢሊዮን ዶላር የሚደርስ ድጋፍ ለምን አልጠየቁም የሚለውም ተነስቷል። ከዚህ በተጨማሪም በኬንያ የተደረገው ስምምነት በከፍተኛው ፍርድ ቤት እና በፓርላማ በግልፅነት፣ በህዝብ ተሳትፎ እና በጤና መረጃ ጥበቃ በኩል ተገቢው ምርመራ እንዲደረግበት መታገዱን የሚያስታውሰው ጥናት፣ የኢትዮጵያ ስምምነት በምን ያህል የፓርላማ እና የህግ ባለሙያዎች ምርመራና ይሁንታ አለፈ የሚለውን ይጠይቃል።
የሀገር ውስጥ የመድኃኒት ምርት እና የህዝብ ተቋማት እውነታ
ሌላው በጥናቱ የተነሳው አሳሳቢ ጉዳይ የመድኃኒት አቅርቦት እና የሀገር ውስጥ ምርት እውነታ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ በሐምሌ ወር ለፓርላማ ባደረጉት ንግግር የሀገር ውስጥ የመድኃኒት ምርት አቅም የሀገሪቱን 44 በመቶ ፍላጎት መሸፈን መቻሉን ገልጸው ነበር። ይሁን እንጂ በጥናቱ እንደተመላከተው፣ ይህ ቁጥር በወረቀት ላይ የሚታይ እንጂ በህዝብ የጤና ተቋማት ውስጥ ያለውን የመድኃኒት እጥረት አይገልጽም።
በጥራዝ ነጠቅ መረጃዎች እና በህሙማን ቅሬታዎች እንደታየው፣ የማህበረሰብ አቀፍ የጤና መድህን ክፍያ የሚከፍሉ ወደ 32 ሚሊዮን የሚጠጉ ዜጎች በመንግስት ሆስፒታሎች መድኃኒት በማጣታቸው ምክንያት ከኪሳቸው ተጨማሪ ገንዘብ አውጥተው ከግል ፋርማሲዎች ለመግዛት ይገደዳሉ። ይህም የመንግስት የሀገር ውስጥ ምርት አድጓል የሚለው መረጃ እና በምድር ላይ ያለው እውነታ አለመጣጣሙን ያሳያል።
የመልካም አስተዳደር እና የታማኝነት ጥያቄዎች
ጥናቱ ሲያጠቃልል ደግሞ የጤና ዘርፍ አመራር እና ስኬት መመዘን ያለበት በሚያምሩ ንግግሮች ወይም ስምምነቶች በመፈራረም ሳይሆን በዜጎች ህይወት ላይ በሚያመጣው ተጨባጭ ለውጥ መሆኑን ያሰምርበታል። የጤና ሚኒስቴር ለፓርላማ እና ለጠቅላይ ሚኒስትሩ የሚያቀርባቸው የቁጥር ሪፖርቶች እውነተኝነት በገለልተኛ አካል ሊረጋገጥ እንደሚገባ የተገለጸ ሲሆን፣ የመድኃኒት አቅርቦት እጥረትን ለማስወገድ እና በህዝብ የጤና ተቋማት ላይ እምነትን ለመመለስ ግልፅ አሰራር እና ቁጥጥር ሊኖር እንደሚገባ በጥናቱ አሳስቧል።
የስምምነቱ ዝርዝር እና የኬንያ ንፅፅር
በታህሳስ 2018 (ዲሴምበር 2025) በጤና ሚኒስትሯ ዶ/ር መቅደስ ዳባ፣ በፋይናንስ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ እና በአሜሪካው አምባሳደር ኤርቪን ማሲንጋ መካከል የተፈረመው ይህ ስምምነት፣ አሜሪካ እስከ 1.166 ቢሊዮን ዶላር (ተጨማሪ የብቃት ድጋፍን ጨምሮ) እና ኢትዮጵያ 450 ሚሊዮን ዶላር በሀገር ውስጥ የሚሸፍኑበት ነው። ነገር ግን ጥናቱ እንደሚያሳየው፣ አጠቃላይ የህዝብ ብዛቷ የኢትዮጵያን ግማሽ ያህል የምትሆነው ጎረቤት ሀገር ኬንያ፣ በተመሳሳይ ጊዜ ከዩናይትድ ስቴትስ ጋር የ2.5 ቢሊዮን ዶላር ስምምነት ተፈራርማለች።
የኢትዮጵያ የህዝብ ብዛት እጅግ የበዛ ሆኖ እያለ፣ ለምን ከኬንያ በእጅጉ ያነሰ የፋይናንስ ድጋፍ ለመቀበል ተስማማች የሚለው ጥያቄ የሙያተኞችን ትኩረት ስቧል። የኢትዮጵያ ተደራዳሪዎች ከህዝብ ብዛታቸው አኳያ ከኬንያ እጥፍ ወይም እስከ 5 ቢሊዮን ዶላር የሚደርስ ድጋፍ ለምን አልጠየቁም የሚለውም ተነስቷል። ከዚህ በተጨማሪም በኬንያ የተደረገው ስምምነት በከፍተኛው ፍርድ ቤት እና በፓርላማ በግልፅነት፣ በህዝብ ተሳትፎ እና በጤና መረጃ ጥበቃ በኩል ተገቢው ምርመራ እንዲደረግበት መታገዱን የሚያስታውሰው ጥናት፣ የኢትዮጵያ ስምምነት በምን ያህል የፓርላማ እና የህግ ባለሙያዎች ምርመራና ይሁንታ አለፈ የሚለውን ይጠይቃል።
የሀገር ውስጥ የመድኃኒት ምርት እና የህዝብ ተቋማት እውነታ
ሌላው በጥናቱ የተነሳው አሳሳቢ ጉዳይ የመድኃኒት አቅርቦት እና የሀገር ውስጥ ምርት እውነታ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ በሐምሌ ወር ለፓርላማ ባደረጉት ንግግር የሀገር ውስጥ የመድኃኒት ምርት አቅም የሀገሪቱን 44 በመቶ ፍላጎት መሸፈን መቻሉን ገልጸው ነበር። ይሁን እንጂ በጥናቱ እንደተመላከተው፣ ይህ ቁጥር በወረቀት ላይ የሚታይ እንጂ በህዝብ የጤና ተቋማት ውስጥ ያለውን የመድኃኒት እጥረት አይገልጽም።
በጥራዝ ነጠቅ መረጃዎች እና በህሙማን ቅሬታዎች እንደታየው፣ የማህበረሰብ አቀፍ የጤና መድህን ክፍያ የሚከፍሉ ወደ 32 ሚሊዮን የሚጠጉ ዜጎች በመንግስት ሆስፒታሎች መድኃኒት በማጣታቸው ምክንያት ከኪሳቸው ተጨማሪ ገንዘብ አውጥተው ከግል ፋርማሲዎች ለመግዛት ይገደዳሉ። ይህም የመንግስት የሀገር ውስጥ ምርት አድጓል የሚለው መረጃ እና በምድር ላይ ያለው እውነታ አለመጣጣሙን ያሳያል።
የመልካም አስተዳደር እና የታማኝነት ጥያቄዎች
ጥናቱ ሲያጠቃልል ደግሞ የጤና ዘርፍ አመራር እና ስኬት መመዘን ያለበት በሚያምሩ ንግግሮች ወይም ስምምነቶች በመፈራረም ሳይሆን በዜጎች ህይወት ላይ በሚያመጣው ተጨባጭ ለውጥ መሆኑን ያሰምርበታል። የጤና ሚኒስቴር ለፓርላማ እና ለጠቅላይ ሚኒስትሩ የሚያቀርባቸው የቁጥር ሪፖርቶች እውነተኝነት በገለልተኛ አካል ሊረጋገጥ እንደሚገባ የተገለጸ ሲሆን፣ የመድኃኒት አቅርቦት እጥረትን ለማስወገድ እና በህዝብ የጤና ተቋማት ላይ እምነትን ለመመለስ ግልፅ አሰራር እና ቁጥጥር ሊኖር እንደሚገባ በጥናቱ አሳስቧል።
3 days ago
በየዓመቱ በዓለም አቀፍ ደረጃ ከ60 ሚሊዮን በላይ ሰዎች ህይወታቸውን ያጣሉ
#ethiopia | በየዓመቱ በዓለም አቀፍ ደረጃ ከ60 ሚሊዮን በላይ ሰዎች በተለያዩ ምክንያቶች ህይወታቸውን እንደሚያጡ መረጃዎች ጠቁመዋል።
የሞት ምጣኔ በሀገራት መካከል በከፍተኛ ሁኔታ የሚለያይ ሲሆን ዋና ዋና ምክንያቶቹ የዕድሜ ስብጥር የአረጋውያን ቁጥር መብዛት ደካማ የጤና ስርዓት ጦርነትና ግጭት ዋነኞቹ ናቸው።
ከሰሀራ በታች ባሉ ሀገራት እንደ ድህነት ያሉ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጽዕኖዎች ለሞት ምጣኔው ከፍተኛ መሆን እንደምክንያትነት ይጠቀሳሉ።
በተጨማሪም በሰሃራ በታች ባሉ የአፍሪካ ሀገራት ደግሞ በቂ የህክምና አቅርቦት አለመኖር ተላላፊ በሽታዎች እና የእናቶችና ህፃናት ሞት ምጣኔ ከፍተኛ መሆን ዋና ምክንያቶች ናቸው።
በጦርነት ውስጥ ባሉ ሀገራት የሰው ህይወት ማጣት እና የጤና ተቋማት መውደም የሞት ምጣኔውን ከፍተኛ አድርጎታል።
በምስራቅ አውሮፓ እንደ ቡልጋሪያ እና ላቲቪያ ያለው የሞት ምጣኔ በቁጥር ከፍ ብሎ የሚታየው አረጋውያን በመብዛታቸው ምክንያት ነው ተብሏል።
ሔኖክ ወ/ገብርኤል
#ethiopia #getutemesgen #getunews #worldpopulation #deathrate #europe #africa
#ethiopia | በየዓመቱ በዓለም አቀፍ ደረጃ ከ60 ሚሊዮን በላይ ሰዎች በተለያዩ ምክንያቶች ህይወታቸውን እንደሚያጡ መረጃዎች ጠቁመዋል።
የሞት ምጣኔ በሀገራት መካከል በከፍተኛ ሁኔታ የሚለያይ ሲሆን ዋና ዋና ምክንያቶቹ የዕድሜ ስብጥር የአረጋውያን ቁጥር መብዛት ደካማ የጤና ስርዓት ጦርነትና ግጭት ዋነኞቹ ናቸው።
ከሰሀራ በታች ባሉ ሀገራት እንደ ድህነት ያሉ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጽዕኖዎች ለሞት ምጣኔው ከፍተኛ መሆን እንደምክንያትነት ይጠቀሳሉ።
በተጨማሪም በሰሃራ በታች ባሉ የአፍሪካ ሀገራት ደግሞ በቂ የህክምና አቅርቦት አለመኖር ተላላፊ በሽታዎች እና የእናቶችና ህፃናት ሞት ምጣኔ ከፍተኛ መሆን ዋና ምክንያቶች ናቸው።
በጦርነት ውስጥ ባሉ ሀገራት የሰው ህይወት ማጣት እና የጤና ተቋማት መውደም የሞት ምጣኔውን ከፍተኛ አድርጎታል።
በምስራቅ አውሮፓ እንደ ቡልጋሪያ እና ላቲቪያ ያለው የሞት ምጣኔ በቁጥር ከፍ ብሎ የሚታየው አረጋውያን በመብዛታቸው ምክንያት ነው ተብሏል።
ሔኖክ ወ/ገብርኤል
#ethiopia #getutemesgen #getunews #worldpopulation #deathrate #europe #africa
3 days ago
(ዘ-ሐበሻ ስፖርት) የ'ሪያል ማድሪድ ፋውንዴሽን' በተጠናቀቀው የውድድር ዘመን በመላው አፍሪካ ካከናወናቸው ስኬታማ ተግባራት መካከል በኢትዮጵያ አዲስ የማህበራዊ ስፖርት አካዳሚ መክፈቱ በዋና ማሳያነት ተጠቅሷል። ፋውንዴሽኑ ኢትዮጵያን ጨምሮ በ23 የአፍሪካ ሀገራት ውስጥ 52 የማህበራዊ ስፖርት ፕሮጀክቶችን ያካሄደ ሲሆን፣ በዚህም 10,628 የሚሆኑ ህጻናትን፣ ታዳጊዎችን እና ወጣቶችን የዕድሉ ተጠቃሚ ማድረግ ችሏል።
በዘመኑ ከተመዘገቡት ትልልቅ ስኬቶች አንዱ በሀገራችን ኢትዮጵያ አዲስ የማህበራዊ ስፖርት አካዳሚ መከፈቱ ነው። ከኢትዮጵያ በተጨማሪም አንጎላ፣ ኬንያ፣ ዩጋንዳ፣ ታንዛኒያ፣ ሴኔጋል እና ግብጽን ጨምሮ በ23 የአፍሪካ ሀገራት ፕሮጀክቱ ተደራሽ ሆኗል።
በአካታችነት በኩል ፋውንዴሽኑ ሴት ታዳጊዎች በስፖርቱ ያላቸውን ተሳትፎ በማሳደግ እና ሴት አሰልጣኞችን በማበረታታት ላይ ልዩ ትኩረት ሰጥቷል። ከዚህም በተጨማሪ አካል ጉዳተኛ ህጻናት፣ ወጣት ስደተኞች እንዲሁም በከባድ ድህነት እና በግጭት የተጎዱ ማህበረሰቦችን የዕድሉ ተጠቃሚ አድርጓል። ከስፖርታዊ እንቅስቃሴዎች ባሻገር ትምህርታዊ ድጋፍን፣ ጤናማ የአኗኗር ዘይቤን፣ የህጻናት ጥበቃን፣ የጾታ እኩልነትን እና ማህበረሰባዊ ትስስርን ማጠናከር የትምህርት ቤቶቹ ዋነኛ የትኩረት አቅጣጫዎች ናቸው።
የአካባቢውን አሰልጣኞች አቅም በስልጠና፣ በክትትል እና በተሞክሮ ልውውጥ ማሳደግ የፕሮጀክቱ ሌላኛው ስኬት ነው። ይህ አካሄድ ከዚህ ቀደም የፕሮጀክቱ ተጠቃሚ የነበሩ ወጣቶች አሁን ላይ ለተተኪው ትውልድ አሰልጣኝ እና አርአያ የሚሆኑበትን ቀጣይነት ያለው ሞዴል ለመፍጠር አስችሏል።
ፋውንዴሽኑ ይህንን ዘላቂ እና አዎንታዊ ተጽዕኖ ለማምጣት ከተለያዩ ማህበራዊ ተቋማት፣ የኃይማኖት ተቋማት፣ ሌሎች ፋውንዴሽኖች፣ ኩባንያዎች እና የአካባቢው መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ጋር በቅንጅት ሲሰራ መቆየቱን አስታውቋል።
በዘመኑ ከተመዘገቡት ትልልቅ ስኬቶች አንዱ በሀገራችን ኢትዮጵያ አዲስ የማህበራዊ ስፖርት አካዳሚ መከፈቱ ነው። ከኢትዮጵያ በተጨማሪም አንጎላ፣ ኬንያ፣ ዩጋንዳ፣ ታንዛኒያ፣ ሴኔጋል እና ግብጽን ጨምሮ በ23 የአፍሪካ ሀገራት ፕሮጀክቱ ተደራሽ ሆኗል።
በአካታችነት በኩል ፋውንዴሽኑ ሴት ታዳጊዎች በስፖርቱ ያላቸውን ተሳትፎ በማሳደግ እና ሴት አሰልጣኞችን በማበረታታት ላይ ልዩ ትኩረት ሰጥቷል። ከዚህም በተጨማሪ አካል ጉዳተኛ ህጻናት፣ ወጣት ስደተኞች እንዲሁም በከባድ ድህነት እና በግጭት የተጎዱ ማህበረሰቦችን የዕድሉ ተጠቃሚ አድርጓል። ከስፖርታዊ እንቅስቃሴዎች ባሻገር ትምህርታዊ ድጋፍን፣ ጤናማ የአኗኗር ዘይቤን፣ የህጻናት ጥበቃን፣ የጾታ እኩልነትን እና ማህበረሰባዊ ትስስርን ማጠናከር የትምህርት ቤቶቹ ዋነኛ የትኩረት አቅጣጫዎች ናቸው።
የአካባቢውን አሰልጣኞች አቅም በስልጠና፣ በክትትል እና በተሞክሮ ልውውጥ ማሳደግ የፕሮጀክቱ ሌላኛው ስኬት ነው። ይህ አካሄድ ከዚህ ቀደም የፕሮጀክቱ ተጠቃሚ የነበሩ ወጣቶች አሁን ላይ ለተተኪው ትውልድ አሰልጣኝ እና አርአያ የሚሆኑበትን ቀጣይነት ያለው ሞዴል ለመፍጠር አስችሏል።
ፋውንዴሽኑ ይህንን ዘላቂ እና አዎንታዊ ተጽዕኖ ለማምጣት ከተለያዩ ማህበራዊ ተቋማት፣ የኃይማኖት ተቋማት፣ ሌሎች ፋውንዴሽኖች፣ ኩባንያዎች እና የአካባቢው መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ጋር በቅንጅት ሲሰራ መቆየቱን አስታውቋል።
3 days ago
በአሜሪካ በሳይክሎስፖሪያሲስ (Cyclosporiasis) ወረርሽኝ የመጀመሪያ ሞት ተመዘገበ
#ethiopia | አሜሪካ ውስጥ በCyclospora cayetanensis ተውሳክ የሚከሰተው የሳይክሎስፖሪያሲስ (Cyclosporiasis) ወረርሽኝ ከተጀመረ በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ከዚህ በሽታ ጋር በተያያዘ ሁለት ሰዎች በሚሺጋን ግዛት መሞታቸውን የግዛቱ የጤና ባለሥልጣናት አስታውቀዋል። ይህ በአሜሪካ ታሪክ ከዚህ ወረርሽኝ ጋር በተያያዘ የተመዘገበ የመጀመሪያው የሞት ክስተት ነው።
ባለሥልጣናቱ እንደገለጹት፣ ሁለቱም ሟቾች ከዚህ ቀደም ከባድ የጤና ችግሮች የነበሯቸው ሲሆን፣ በተደጋጋሚ ተቅማጥና በውኃ እጥረት (dehydration) ምክንያት የነበራቸው ሁኔታ ተባብሶ ለሞት እንዳደረሳቸው ተገልጿል። የግል መረጃቸው አልተገለጸም።
በሚሺጋን ግዛት ብቻ እስካሁን ከ11,000 በላይ ተጠርጣሪ ወይም የተመዘገቡ ኬሶች ሲኖሩ፣ 193 ሰዎች ሆስፒታል ገብተዋል። በመላው አሜሪካ ደግሞ ከ6,700 በላይ በላብራቶሪ የተረጋገጡ ኬሶች ተመዝግበዋል፣ ተጨማሪ ብዙ ሺህ ጉዳዮችም እየተመረመሩ ይገኛሉ።
የበሽታው ምንጭ ምንድን ነው?
የአሜሪካ የበሽታ መከላከልና መቆጣጠሪያ ማዕከል (CDC) እና የምግብና መድኃኒት ባለሥልጣን (FDA) እያካሄዱት ባለው ምርመራ፣ ወረርሽኙ በዋነኝነት ከተበከለ የአይስበርግ ሰላጣ (iceberg lettuce) ጋር የተያያዘ ሊሆን እንደሚችል ተጠርጥሯል። ሆኖም ምርመራው አሁንም በመቀጠል ላይ ሲሆን የመጨረሻ ማረጋገጫ አልተሰጠም።
የበሽታው ምልክቶች
ከባድ የውኃ ተቅማጥ
የሆድ ህመም
ማቅለሽለሽ
ድካም
የምግብ ፍላጎት መቀነስ
አንዳንድ ጊዜ ትኩሳት
በጤናማ ሰዎች ላይ በአብዛኛው ሕክምና በመውሰድ ይድናል፤ ነገር ግን አረጋውያን፣ የበሽታ መከላከያ አቅማቸው ዝቅተኛ የሆኑ ሰዎች እና ሌሎች ከባድ የጤና ችግሮች ያሉባቸው ሰዎች ለከፍተኛ አደጋ ሊጋለጡ ይችላሉ።
የጤና ባለሥልጣናት የሰጡት ምክር
ጥሬ አትክልቶችንና ፍራፍሬዎችን በደንብ በማጠብ ይጠቀሙ።
የተጠረጠሩ የሰላጣ ምርቶችን አይጠቀሙ።
ተቅማጥ ከቀጠለ ወይም የውኃ እጥረት ምልክቶች ከታዩ በፍጥነት ወደ ጤና ተቋም ይሂዱ።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#ethiopia | አሜሪካ ውስጥ በCyclospora cayetanensis ተውሳክ የሚከሰተው የሳይክሎስፖሪያሲስ (Cyclosporiasis) ወረርሽኝ ከተጀመረ በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ከዚህ በሽታ ጋር በተያያዘ ሁለት ሰዎች በሚሺጋን ግዛት መሞታቸውን የግዛቱ የጤና ባለሥልጣናት አስታውቀዋል። ይህ በአሜሪካ ታሪክ ከዚህ ወረርሽኝ ጋር በተያያዘ የተመዘገበ የመጀመሪያው የሞት ክስተት ነው።
ባለሥልጣናቱ እንደገለጹት፣ ሁለቱም ሟቾች ከዚህ ቀደም ከባድ የጤና ችግሮች የነበሯቸው ሲሆን፣ በተደጋጋሚ ተቅማጥና በውኃ እጥረት (dehydration) ምክንያት የነበራቸው ሁኔታ ተባብሶ ለሞት እንዳደረሳቸው ተገልጿል። የግል መረጃቸው አልተገለጸም።
በሚሺጋን ግዛት ብቻ እስካሁን ከ11,000 በላይ ተጠርጣሪ ወይም የተመዘገቡ ኬሶች ሲኖሩ፣ 193 ሰዎች ሆስፒታል ገብተዋል። በመላው አሜሪካ ደግሞ ከ6,700 በላይ በላብራቶሪ የተረጋገጡ ኬሶች ተመዝግበዋል፣ ተጨማሪ ብዙ ሺህ ጉዳዮችም እየተመረመሩ ይገኛሉ።
የበሽታው ምንጭ ምንድን ነው?
የአሜሪካ የበሽታ መከላከልና መቆጣጠሪያ ማዕከል (CDC) እና የምግብና መድኃኒት ባለሥልጣን (FDA) እያካሄዱት ባለው ምርመራ፣ ወረርሽኙ በዋነኝነት ከተበከለ የአይስበርግ ሰላጣ (iceberg lettuce) ጋር የተያያዘ ሊሆን እንደሚችል ተጠርጥሯል። ሆኖም ምርመራው አሁንም በመቀጠል ላይ ሲሆን የመጨረሻ ማረጋገጫ አልተሰጠም።
የበሽታው ምልክቶች
ከባድ የውኃ ተቅማጥ
የሆድ ህመም
ማቅለሽለሽ
ድካም
የምግብ ፍላጎት መቀነስ
አንዳንድ ጊዜ ትኩሳት
በጤናማ ሰዎች ላይ በአብዛኛው ሕክምና በመውሰድ ይድናል፤ ነገር ግን አረጋውያን፣ የበሽታ መከላከያ አቅማቸው ዝቅተኛ የሆኑ ሰዎች እና ሌሎች ከባድ የጤና ችግሮች ያሉባቸው ሰዎች ለከፍተኛ አደጋ ሊጋለጡ ይችላሉ።
የጤና ባለሥልጣናት የሰጡት ምክር
ጥሬ አትክልቶችንና ፍራፍሬዎችን በደንብ በማጠብ ይጠቀሙ።
የተጠረጠሩ የሰላጣ ምርቶችን አይጠቀሙ።
ተቅማጥ ከቀጠለ ወይም የውኃ እጥረት ምልክቶች ከታዩ በፍጥነት ወደ ጤና ተቋም ይሂዱ።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
Sponsored by
Surafel
3 days ago
በኦቶና ሆስፒታል የላብራቶሪ መሳሪያዎችን ሊሰርቅ የነበረ የጥበቃ ሰራተኛ እጅ ከፍንጂ ተያዘ
በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ኮምፕሬሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል (ኦቶና) ሦስት ወሳኝ የላብራቶሪ ማይክሮስኮፖችን አውጥቶ ለመሰወር ሲሞክር የነበረ የጥበቃ ሰራተኛ በተረኛ ጥበቃዎች ብርቱ ክትትልና ተጋድሎ እጅ ከፍንጂ መያዙ ተገለጸ።
በትላትናው እለተ የተፈጸመው ይህ ድርጊት ተራ የሕክምና ዕቃ ስርቆት ሳይሆን፣ የሺዎችን ሕይወት እና የሆስፒታሉን ዕለታዊ የሕክምና አገልግሎት ቀጥተኛ አደጋ ላይ የጣለ ከባድ ወንጀል መሆኑን ባለሙያዎች ይናገራሉ።
ተጠርጣሪው ግለሰብ የሕክምና መገልገያዎቹን ደብቆ ከሆስፒታሉ ግቢ ሊያወጣ ሲል በተረኛ ባልደረቦቹ ንቁ ክትትል በቁጥጥር ስር ውሏል። ድርጊቱ በግለሰቡ ብቻ የተፈጸመ ሳይሆን በጀርባ ያሉ አመቻቾችና አቀናባሪዎች እንዳሉበት በመጠረጠሩ፣ ወንጀሉን ያስተባበሩ አካላት በሙሉ ተለይተው ተገቢው የሕግ ትርጉም እንዲሰጣቸውና አስተማሪ ቅጣት እንዲያገኙ ጉዳዩ በትኩረት እየተከታተለ ይገኛል።
በአንድ አጠቃላይ ሆስፒታል ውስጥ ማይክሮስኮፕ ማለት የተደበቁ በሽታዎችን አውጥቶ በማሳየት የሕሙማንን ሕይወት የሚያስጥል ዋና መመርመሪያ መሳሪያ ነው።
እነዚህን መገልገያዎች ማጣት በሕሙማን ላይ የሚከተሉትን ከባድ የጤና አደጋዎች ያስከትላል፦
እንደ ወባ፣ ቲቢ እና የተለያዩ ከባድ የባክቴሪያ ኢንፌክሽኖችን በፍጥነት በመመርመር አስቸኳይ የሕክምና ውሳኔ ለመስጠት ያገለግላሉ።
የደም ማነስን (Anemia) እና የደም ካንሰርን (Leukemia) በጥንቃቄ ለይቶ ለማወቅ ወሳኝ መገልገያዎች ናቸው።
እነዚህ መሳሪያዎች ከአገልግሎት ውጭ ሲሆኑ የላብራቶሪ ውጤቶች ይዘገያሉ፤ ይህም በተለይ በፅኑ ሕሙማን፣ በሕፃናትና ነፍሰ ጡራት ሕይወት ላይ የቀጥታ አደጋ ይደቅናል።
የሕዝብና የመንግሥት ሀብት የሆኑትን የሕክምና መገልገያዎች ከስርቆትና ከእጅ አዙር ሴራ መጠበቅ የሁላችንም ኃላፊነት ነው።
በሆስፒታሉ ግቢ ውስጥ የታየው የተረኛ ጥበቃዎች ንቅናቄ የሚደነቅ ሲሆን፣ የወንጀሉ ተሳታፊዎች በሙሉ ለሕግ እንዲቀርቡ የጀመረው ክትትል ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል።
Via ጉርሻ page
በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ኮምፕሬሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል (ኦቶና) ሦስት ወሳኝ የላብራቶሪ ማይክሮስኮፖችን አውጥቶ ለመሰወር ሲሞክር የነበረ የጥበቃ ሰራተኛ በተረኛ ጥበቃዎች ብርቱ ክትትልና ተጋድሎ እጅ ከፍንጂ መያዙ ተገለጸ።
በትላትናው እለተ የተፈጸመው ይህ ድርጊት ተራ የሕክምና ዕቃ ስርቆት ሳይሆን፣ የሺዎችን ሕይወት እና የሆስፒታሉን ዕለታዊ የሕክምና አገልግሎት ቀጥተኛ አደጋ ላይ የጣለ ከባድ ወንጀል መሆኑን ባለሙያዎች ይናገራሉ።
ተጠርጣሪው ግለሰብ የሕክምና መገልገያዎቹን ደብቆ ከሆስፒታሉ ግቢ ሊያወጣ ሲል በተረኛ ባልደረቦቹ ንቁ ክትትል በቁጥጥር ስር ውሏል። ድርጊቱ በግለሰቡ ብቻ የተፈጸመ ሳይሆን በጀርባ ያሉ አመቻቾችና አቀናባሪዎች እንዳሉበት በመጠረጠሩ፣ ወንጀሉን ያስተባበሩ አካላት በሙሉ ተለይተው ተገቢው የሕግ ትርጉም እንዲሰጣቸውና አስተማሪ ቅጣት እንዲያገኙ ጉዳዩ በትኩረት እየተከታተለ ይገኛል።
በአንድ አጠቃላይ ሆስፒታል ውስጥ ማይክሮስኮፕ ማለት የተደበቁ በሽታዎችን አውጥቶ በማሳየት የሕሙማንን ሕይወት የሚያስጥል ዋና መመርመሪያ መሳሪያ ነው።
እነዚህን መገልገያዎች ማጣት በሕሙማን ላይ የሚከተሉትን ከባድ የጤና አደጋዎች ያስከትላል፦
እንደ ወባ፣ ቲቢ እና የተለያዩ ከባድ የባክቴሪያ ኢንፌክሽኖችን በፍጥነት በመመርመር አስቸኳይ የሕክምና ውሳኔ ለመስጠት ያገለግላሉ።
የደም ማነስን (Anemia) እና የደም ካንሰርን (Leukemia) በጥንቃቄ ለይቶ ለማወቅ ወሳኝ መገልገያዎች ናቸው።
እነዚህ መሳሪያዎች ከአገልግሎት ውጭ ሲሆኑ የላብራቶሪ ውጤቶች ይዘገያሉ፤ ይህም በተለይ በፅኑ ሕሙማን፣ በሕፃናትና ነፍሰ ጡራት ሕይወት ላይ የቀጥታ አደጋ ይደቅናል።
የሕዝብና የመንግሥት ሀብት የሆኑትን የሕክምና መገልገያዎች ከስርቆትና ከእጅ አዙር ሴራ መጠበቅ የሁላችንም ኃላፊነት ነው።
በሆስፒታሉ ግቢ ውስጥ የታየው የተረኛ ጥበቃዎች ንቅናቄ የሚደነቅ ሲሆን፣ የወንጀሉ ተሳታፊዎች በሙሉ ለሕግ እንዲቀርቡ የጀመረው ክትትል ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል።
Via ጉርሻ page
3 days ago
የጤናው ዘርፍ የአረንጓዴ አሻራ ተሳትፎ
📌 ከ30 ሺህ በላይ ችግኞች በዛሬው እለት ተተክለዋል
#ethiopia | በሀገር አቀፍ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር ላይ የጤና ሚኒስቴር እና የተጠሪ ተቋማት አመራሮች እንዲሁም ሰራተኞች ከኢትዮጵያ የአካል ድጋፍ አገልግሎት ከገፈርሳ ጉጄ ክፍለ ከተማ ጋር በመተባበር በዛሬ እለት በገፈርሳ ሰው ሰራሽ ሀይቅ ዳርቻ ከ30 ሺህ በላይ ችግኞች በዛሬው እለት ተተክለዋል።
በሸገር ከተማ በገፈርሳ ጉጄ አካባቢ በተካሄደው በዚህ የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር ላይ የጤና ሚኒስትሯ ክብርት ዶክተር መቅደስ ዳባ፣ ሚኒስትር ዴኤታዎች እና የየደረጃው የአካባቢው አመራሮች እንዲሁም የሀገር መከላከያ ሰራዊት አባላትና የማህበረሰብ ክፍሎች ከማለዳው 1 ሰዓት ጀምሮ በመገኘት ችግኝ ተክለዋል።
የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ደረጄ ዱጉማ በዚሁ ወቅት ባደረጉት ንግግር፣ አረንጓዴ አሻራ እና የጤና ዘርፍ የማይለያዩ የአንድ ሳንቲም ሁለት ገጽታዎች መሆናቸውን ገልጸዋል። ችግኝ ለአካባቢ ጥበቃ ብቻ ሳይሆን ለህብረተሰብ ጤና፣ ለንጹህ አየር እና ለምግብ ዋስትና ማሻሻያ ወሳኝ ሚና እንደሚጫወት የጠቆሙት ሚኒስትር ዴኤታው፣ በተለይም ለአዲስ አበባ እና ለአካባቢው ህዝብ የንጹህ ውሃ ምንጭ የሆነውን የገፈርሳ አካባቢን መንከባከብ የሁላችንም ህብረ-ብሄራዊ ሀገራዊ ኃላፊነት እንደሆነ አስገንዝበዋል።
በዕለቱ በቦታው ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የጤና ሚኒስትሯ ክብርት ዶክተር መቅደስ ዳባ በበኩላቸው፣ ኢትዮጵያ የተፈጥሮ አካባቢዋን ለመጠበቅ የምታደርገው ጥረት በንግግር ሳይሆን በተግባር የሚገለጽ መሆኑን አብራርተዋል።
በዕለቱ ሚኒስቴሩ ከተጠሪ ተቋማት ጋር በመሆን ከ30 ሺህ በላይ ችግኞችን የተከለ ሲሆን፣ በክረምቱ የክረምት በጎ ፈቃድ መርሃ-ግብር ደግሞ በሀገር አቀፍ ደረጃ እስከ 250 ሺህ ችግኞችን ለመትከል እና ከ20 ሚሊዮን በላይ ዜጎችን ነጻ የህክምና አገልግሎት ለመስጠት ታቅዶ እየተሰራ እንደሚገኝ ሚኒስትሯ ገልጸዋል።
በመጨረሻም ክብርት ሚኒስትሯ፣ የጤና ባለሙያዎች እና መላው የሀገራችን ህዝብ ቀኑ ሳያልቅ እና ጀምበር ሳትጠልቅ የድርሻቸውን ችግኝ በመትከል የዚህ ታሪካዊ ኩነት አካል እንዲሆኑ ጥሪ አቅርበዋል።
ከችግኝ ተከላው መርሐግብር ባሻገር የኢትዮጵያ የአካል ድጋፍ አገልግሎት በሸገር ከተማ ከ200 በላይ ለሚሆኑ ተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ ተደርጓል።
በጌትነት ተመስገን
📷 ከበደ መክብብ
#ministryofhealth #treeplanting
#climateaction #publichealth
#environmentalhealth #gefersa #cleanenvironment #greenethiopia
#communitysupport
📌 ከ30 ሺህ በላይ ችግኞች በዛሬው እለት ተተክለዋል
#ethiopia | በሀገር አቀፍ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር ላይ የጤና ሚኒስቴር እና የተጠሪ ተቋማት አመራሮች እንዲሁም ሰራተኞች ከኢትዮጵያ የአካል ድጋፍ አገልግሎት ከገፈርሳ ጉጄ ክፍለ ከተማ ጋር በመተባበር በዛሬ እለት በገፈርሳ ሰው ሰራሽ ሀይቅ ዳርቻ ከ30 ሺህ በላይ ችግኞች በዛሬው እለት ተተክለዋል።
በሸገር ከተማ በገፈርሳ ጉጄ አካባቢ በተካሄደው በዚህ የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር ላይ የጤና ሚኒስትሯ ክብርት ዶክተር መቅደስ ዳባ፣ ሚኒስትር ዴኤታዎች እና የየደረጃው የአካባቢው አመራሮች እንዲሁም የሀገር መከላከያ ሰራዊት አባላትና የማህበረሰብ ክፍሎች ከማለዳው 1 ሰዓት ጀምሮ በመገኘት ችግኝ ተክለዋል።
የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ደረጄ ዱጉማ በዚሁ ወቅት ባደረጉት ንግግር፣ አረንጓዴ አሻራ እና የጤና ዘርፍ የማይለያዩ የአንድ ሳንቲም ሁለት ገጽታዎች መሆናቸውን ገልጸዋል። ችግኝ ለአካባቢ ጥበቃ ብቻ ሳይሆን ለህብረተሰብ ጤና፣ ለንጹህ አየር እና ለምግብ ዋስትና ማሻሻያ ወሳኝ ሚና እንደሚጫወት የጠቆሙት ሚኒስትር ዴኤታው፣ በተለይም ለአዲስ አበባ እና ለአካባቢው ህዝብ የንጹህ ውሃ ምንጭ የሆነውን የገፈርሳ አካባቢን መንከባከብ የሁላችንም ህብረ-ብሄራዊ ሀገራዊ ኃላፊነት እንደሆነ አስገንዝበዋል።
በዕለቱ በቦታው ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የጤና ሚኒስትሯ ክብርት ዶክተር መቅደስ ዳባ በበኩላቸው፣ ኢትዮጵያ የተፈጥሮ አካባቢዋን ለመጠበቅ የምታደርገው ጥረት በንግግር ሳይሆን በተግባር የሚገለጽ መሆኑን አብራርተዋል።
በዕለቱ ሚኒስቴሩ ከተጠሪ ተቋማት ጋር በመሆን ከ30 ሺህ በላይ ችግኞችን የተከለ ሲሆን፣ በክረምቱ የክረምት በጎ ፈቃድ መርሃ-ግብር ደግሞ በሀገር አቀፍ ደረጃ እስከ 250 ሺህ ችግኞችን ለመትከል እና ከ20 ሚሊዮን በላይ ዜጎችን ነጻ የህክምና አገልግሎት ለመስጠት ታቅዶ እየተሰራ እንደሚገኝ ሚኒስትሯ ገልጸዋል።
በመጨረሻም ክብርት ሚኒስትሯ፣ የጤና ባለሙያዎች እና መላው የሀገራችን ህዝብ ቀኑ ሳያልቅ እና ጀምበር ሳትጠልቅ የድርሻቸውን ችግኝ በመትከል የዚህ ታሪካዊ ኩነት አካል እንዲሆኑ ጥሪ አቅርበዋል።
ከችግኝ ተከላው መርሐግብር ባሻገር የኢትዮጵያ የአካል ድጋፍ አገልግሎት በሸገር ከተማ ከ200 በላይ ለሚሆኑ ተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ ተደርጓል።
በጌትነት ተመስገን
📷 ከበደ መክብብ
#ministryofhealth #treeplanting
#climateaction #publichealth
#environmentalhealth #gefersa #cleanenvironment #greenethiopia
#communitysupport
3 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የአፍሪካ ህብረት መረጃ እንደሚያመለክተው ቢያንስ 600,000 ሰዎችን ከገደለው ጦርነት ከአራት ዓመት ባነሰ ጊዜ ውስጥ፣ የፌደራል መንግስት ሰራዊት እና የትግራይ ኃይሎች በሰሜን ትግራይ ድንበር አካባቢ ለወራት ኃይል ሲያከማቹ መቆየታቸው ዳግም ጦርነት ሊቀሰቀስ ይችላል የሚለውን ስጋት አባብሶታል። በዚህም መሰረት በድንበር አካባቢ የተቀሰቀሰውን ውጊያ በመሸሽ በመቶዎች የሚቆጠሩ ከሰሜን ትግራይ ክልል የተፈናቀሉ ኢትዮጵያውያን ባለፉት ሁለት ቀናት ውስጥ ወደ ጎረቤት ሱዳን መግባታቸውን የሱዳን የጸጥታ እና የህክምና ምንጮች ለኤኤፍፒ ተናግረዋል። ይህ የስደተኞች ፍሰት የተከሰተው ሱዳን ራሷ ከሚያዝያ 2023 ጀምሮ በሱዳን ጦር እና በፈጣን ድጋፍ ሰጪ ኃይሎች (RSF) መካከል በሚካሄድ አውዳሚ ጦርነት ውስጥ ባለችበት ወቅት ነው።
አንድ የህዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) አባል እንደገለጹት፣ በኢትዮጵያ ጦር እና በትግራይ ኃይሎች መካከል ከባድ የጦር መሳሪያዎች እና ድሮኖች የታከሉበት ውጊያ በምዕራብ ትግራይ፣ ከሱዳን ድንበር አቅራቢያ በምትገኘው ሸረሪና በተባለችው አካባቢ ቅዳሜ ማለዳ ላይ የተቀሰቀሰ ሲሆን፣ እስከ እሁድ ንጋት 11፡00 ሰዓት (5:00 am) ድረስ ቀጥሎ ነበር። ቅዳሜ ዕለት ህወሓት የኢትዮጵያ ፌደራል መንግስትን ሰፋፊ የእግረኛ ጦር ጥቃቶችን ፈጽሞብኛል ሲል የከሰሰ ሲሆን፣ ባለስልጣናት ለዚህ ክስ ወዲያውኑ የሰጡት ምላሽ የለም። ኤኤፍፒ የህወሓትን ክሶች በገለልተኛ ወገን ማረጋገጥም ሆነ በሸረሪና ውጊያ ውስጥ የተሳተፉትን ኃይሎች በግልጽ መለየት አለመቻሉን ዘግቧል።
በድንበር ከተማዋ ሀምዳይት የሚገኝ አንድ የሱዳን የጸጥታ ምንጭ፣ ከትግራይ ወደ ሱዳን ከገቡት ሰዎች መካከል የቆሰሉ ተዋጊዎች እንደሚገኙበት ገልጿል። በድንበር ጤና ጣቢያ የሚገኝ የህክምና ምንጭ እንዳስታወቀው፣ የቆሰሉት ሰዎች የመጀመሪያ ደረጃ የህክምና እርዳታ ከተደረገላቸው በኋላ በ2020-2022 በነበረው የትግራይ ጦርነት የተፈናቀሉ በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ወደሚገኙበት እና 15 ኪሎ ሜትር ሱዳን ውስጥ ወደሚገኘው አል-ሀሻባ ተዛውረዋል። በሱዳን በኩል የሚገኙ የድንበር አካባቢ ነዋሪዎች በውጊያው ወቅት ከባድ ፍንዳታዎች እና ተከታታይ የተኩስ ልውውጦች ሲሰሙ እንደነበር ዘግበዋል።
ከድንበሩ 40 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በምትገኘው ዋድ አል-ሁለይዋ የተባለች መንደር ነዋሪ የሆነ የዓይን እማኝ፣ ቅዳሜ ማለዳ ላይ ሶስት ኃይለኛ ፍንዳታዎችን መስማቱን ተናግሯል። እማኙ አክሎም፣ ከቀኑ 10፡30 ገደማ ላይ ከባድ የተኩስ ድምጽ ይሰማ እንደነበር እና በአቅራቢያው የምትገኘው የአል-ቁዳይማ መንደር ነዋሪዎች የሰቲት ወንዝን አቋርጠው መሸሻቸውን አስረድቷል። በሀምዳይት የሚገኝ ሌላ የዓይን እማኝ በበኩሉ፣ ቅዳሜን ሙሉ ፍንዳታዎች ይሰሙ እንደነበር እና ከሀምዳይት በስተደቡብ ምዕራብ አቅጣጫ አውሮፕላኖች ሲበሩ መመልከቱን ገልጿል።
ይህ የሰሞኑ ግጭት የተከሰተው በኢትዮጵያ እና ሱዳን መካከል ያለው ግንኙነት ሻክሮ በሚገኝበት ወቅት መሆኑ ሁኔታውን ይበልጥ አሳሳቢ ያደርገዋል። ባለፈው ግንቦት ወር ኢትዮጵያ የሱዳን ጦር ከህወሓት ጋር ግንኙነት ያላቸውን ቅጥረኞች ይደግፋል ስትል የከሰሰች ሲሆን፣ ሱዳን በበኩሏ ኢትዮጵያ ከተባበሩት አረብ ኤምሬቶች ጋር በመቀናጀት ከግዛቷ የድሮን ጥቃቶች እንዲፈጸሙ ፈቅዳለች የሚል ክስ አቅርባለች። የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች የቀረበባትን ክስ ብታስተባብልም፣ የፈጣን ድጋፍ ሰጪ ኃይሎች (RSF) ዋነኛ ደጋፊ ናት ተብላ ትከሰሳለች።
አንድ የህዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) አባል እንደገለጹት፣ በኢትዮጵያ ጦር እና በትግራይ ኃይሎች መካከል ከባድ የጦር መሳሪያዎች እና ድሮኖች የታከሉበት ውጊያ በምዕራብ ትግራይ፣ ከሱዳን ድንበር አቅራቢያ በምትገኘው ሸረሪና በተባለችው አካባቢ ቅዳሜ ማለዳ ላይ የተቀሰቀሰ ሲሆን፣ እስከ እሁድ ንጋት 11፡00 ሰዓት (5:00 am) ድረስ ቀጥሎ ነበር። ቅዳሜ ዕለት ህወሓት የኢትዮጵያ ፌደራል መንግስትን ሰፋፊ የእግረኛ ጦር ጥቃቶችን ፈጽሞብኛል ሲል የከሰሰ ሲሆን፣ ባለስልጣናት ለዚህ ክስ ወዲያውኑ የሰጡት ምላሽ የለም። ኤኤፍፒ የህወሓትን ክሶች በገለልተኛ ወገን ማረጋገጥም ሆነ በሸረሪና ውጊያ ውስጥ የተሳተፉትን ኃይሎች በግልጽ መለየት አለመቻሉን ዘግቧል።
በድንበር ከተማዋ ሀምዳይት የሚገኝ አንድ የሱዳን የጸጥታ ምንጭ፣ ከትግራይ ወደ ሱዳን ከገቡት ሰዎች መካከል የቆሰሉ ተዋጊዎች እንደሚገኙበት ገልጿል። በድንበር ጤና ጣቢያ የሚገኝ የህክምና ምንጭ እንዳስታወቀው፣ የቆሰሉት ሰዎች የመጀመሪያ ደረጃ የህክምና እርዳታ ከተደረገላቸው በኋላ በ2020-2022 በነበረው የትግራይ ጦርነት የተፈናቀሉ በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ወደሚገኙበት እና 15 ኪሎ ሜትር ሱዳን ውስጥ ወደሚገኘው አል-ሀሻባ ተዛውረዋል። በሱዳን በኩል የሚገኙ የድንበር አካባቢ ነዋሪዎች በውጊያው ወቅት ከባድ ፍንዳታዎች እና ተከታታይ የተኩስ ልውውጦች ሲሰሙ እንደነበር ዘግበዋል።
ከድንበሩ 40 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በምትገኘው ዋድ አል-ሁለይዋ የተባለች መንደር ነዋሪ የሆነ የዓይን እማኝ፣ ቅዳሜ ማለዳ ላይ ሶስት ኃይለኛ ፍንዳታዎችን መስማቱን ተናግሯል። እማኙ አክሎም፣ ከቀኑ 10፡30 ገደማ ላይ ከባድ የተኩስ ድምጽ ይሰማ እንደነበር እና በአቅራቢያው የምትገኘው የአል-ቁዳይማ መንደር ነዋሪዎች የሰቲት ወንዝን አቋርጠው መሸሻቸውን አስረድቷል። በሀምዳይት የሚገኝ ሌላ የዓይን እማኝ በበኩሉ፣ ቅዳሜን ሙሉ ፍንዳታዎች ይሰሙ እንደነበር እና ከሀምዳይት በስተደቡብ ምዕራብ አቅጣጫ አውሮፕላኖች ሲበሩ መመልከቱን ገልጿል።
ይህ የሰሞኑ ግጭት የተከሰተው በኢትዮጵያ እና ሱዳን መካከል ያለው ግንኙነት ሻክሮ በሚገኝበት ወቅት መሆኑ ሁኔታውን ይበልጥ አሳሳቢ ያደርገዋል። ባለፈው ግንቦት ወር ኢትዮጵያ የሱዳን ጦር ከህወሓት ጋር ግንኙነት ያላቸውን ቅጥረኞች ይደግፋል ስትል የከሰሰች ሲሆን፣ ሱዳን በበኩሏ ኢትዮጵያ ከተባበሩት አረብ ኤምሬቶች ጋር በመቀናጀት ከግዛቷ የድሮን ጥቃቶች እንዲፈጸሙ ፈቅዳለች የሚል ክስ አቅርባለች። የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች የቀረበባትን ክስ ብታስተባብልም፣ የፈጣን ድጋፍ ሰጪ ኃይሎች (RSF) ዋነኛ ደጋፊ ናት ተብላ ትከሰሳለች።
4 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) መብራት የተቋረጠባቸው ሱዳናዊያን መንገድ ዘግተው ዋሉ፡፡ በሱዳን ቀይ ባህር ግዛት የሚገኙ ነዋሪዎች የመብራት አገልግሎት የተቋረጠባቸው መሆኑን ተከትሎ ከአርብ እለት ጀምሮ ተቃውሞ እያሰሙ ይገኛሉ፡፡ ይህ ተቃውሞ በትላንትናው እለትም ቀጥሎ ፖርት ሱዳንን ከዋና ከተማዋ ካርቱም ጋር የሚያገናኘውን መንገድ ዘግተው መዋላቸውን ሱዳን ትሪቢዩን ዘግቧል፡፡
ተቃዋሚዎቹ በግዛታቸው ውስጥ በአሁኑ ወቅት የተከሰተውን ሀይለኛ ሙቀት ከግምት ውስጥ በማስገባት መንግስት የመብራት አገልግሎቱ በአስቸኳይ የሚመለስበትን እርምጃ እንዲወስድ እየጠየቁ ናቸው፡፡ እንደዘገባው በቀይ ባህር ግዛት ከፍተኛ የሙቀት መጠን እየተመዘገበ ሲሆን አንዳንድ ቤተሰቦች ቤታቸውን ጥለው ቀዝቃዛ ወደሆኑ ግዛቶች በመሄድ ላይ ናቸው፡፡ በርካታ የግዛቱ ነዋሪ ግን በተፈጠረው የኤሌክትሪክ መቋረጥ የተነሳ የከፋ ህይወትን ለማሳለፍ ተገደዋል፡፡
አንድ የአካባቢው ነዋሪ ለሱዳን ትሪቢዩን ሲናገሩ የመብራት መጥፋቱ መሰረታዊ አገልግሎቶች እንዲቋረጡ ማድረጉን ገልፀው በከፍተኛ ሙቀት ውስጥ የነዋሪው የእለት ተእለት ኑሮውን የባሰ እንዳደረገው አስረድተዋል፡፡ ነዋሪው ፖርት ሱዳንን ወደዋና ከተማዋና ሌሎችም ማእከላዊ የአገሪቱ ክፍሎች የሚወስደውን ዋና መንገድ ለመዝጋት የተገደደው በዚህ የተነሳ መሆኑንም ገልፀዋል፡፡
ሌላ ስማቸው እንዲገለፅ ያልፈለጉ ነዋሪ በበኩላቸው መንገድ የመዝጋት እርምጃው የተወሰደው ለበርካታ ጊዜ ችግሩ እንዲስተካከል ለመንግስት ያቀረቡት አቤቱታ ምላሽ በማጣቱ መሆኑን ገልፀዋል፡፡ ከፍተኛ ሙቀት ባለበት ሁኔታ የመብራት መቆራረጥ መፈጠሩ በተለይ ህፃናትና አረጋዊያን ላይ የጤና ችግር እያስከተ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡ የሜትሮሎጂ መረጃዎች በቀይ ባህር ግዛት በሚቀጥሉት ቀናትም የሙቀት መጠኑ እንደሚጨምር ይገልፃሉ፡፡
ተቃዋሚዎቹ በግዛታቸው ውስጥ በአሁኑ ወቅት የተከሰተውን ሀይለኛ ሙቀት ከግምት ውስጥ በማስገባት መንግስት የመብራት አገልግሎቱ በአስቸኳይ የሚመለስበትን እርምጃ እንዲወስድ እየጠየቁ ናቸው፡፡ እንደዘገባው በቀይ ባህር ግዛት ከፍተኛ የሙቀት መጠን እየተመዘገበ ሲሆን አንዳንድ ቤተሰቦች ቤታቸውን ጥለው ቀዝቃዛ ወደሆኑ ግዛቶች በመሄድ ላይ ናቸው፡፡ በርካታ የግዛቱ ነዋሪ ግን በተፈጠረው የኤሌክትሪክ መቋረጥ የተነሳ የከፋ ህይወትን ለማሳለፍ ተገደዋል፡፡
አንድ የአካባቢው ነዋሪ ለሱዳን ትሪቢዩን ሲናገሩ የመብራት መጥፋቱ መሰረታዊ አገልግሎቶች እንዲቋረጡ ማድረጉን ገልፀው በከፍተኛ ሙቀት ውስጥ የነዋሪው የእለት ተእለት ኑሮውን የባሰ እንዳደረገው አስረድተዋል፡፡ ነዋሪው ፖርት ሱዳንን ወደዋና ከተማዋና ሌሎችም ማእከላዊ የአገሪቱ ክፍሎች የሚወስደውን ዋና መንገድ ለመዝጋት የተገደደው በዚህ የተነሳ መሆኑንም ገልፀዋል፡፡
ሌላ ስማቸው እንዲገለፅ ያልፈለጉ ነዋሪ በበኩላቸው መንገድ የመዝጋት እርምጃው የተወሰደው ለበርካታ ጊዜ ችግሩ እንዲስተካከል ለመንግስት ያቀረቡት አቤቱታ ምላሽ በማጣቱ መሆኑን ገልፀዋል፡፡ ከፍተኛ ሙቀት ባለበት ሁኔታ የመብራት መቆራረጥ መፈጠሩ በተለይ ህፃናትና አረጋዊያን ላይ የጤና ችግር እያስከተ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡ የሜትሮሎጂ መረጃዎች በቀይ ባህር ግዛት በሚቀጥሉት ቀናትም የሙቀት መጠኑ እንደሚጨምር ይገልፃሉ፡፡
4 days ago
የውኃ ሉዓላዊነታችን በተግባር፡ ከ18 ዓመታት የእንቅልፍ ዘመን የነቃው የመገጭ ግድብ
****************
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን ጋር ባደረጉት ቆይታ በአማራ ክልል እየተከናወኑ ያሉ ታላላቅ የልማት ፕሮጀክቶችን በተመለከተ ሰፊ ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡
ከእነዚህ ሀገራዊ ፕሮጀክቶች መካከል የጎንደር ከተማ ነዋሪዎችን የረዥም ዘመን የመጠጥ ውኃ ጥያቄ የሚመልሰው እና ሰፊ የመስኖ ልማት አቅም ያለው የመገጭ ግድብ በግንባር ቀደምትነት ይጠቀሳል፡፡
ግንባታው በ2001 ዓ.ም. የተጀመረው ይህ ግድብ፣ ላለፉት 18 ዓመታት የመልካም አስተዳደር እና የፕሮጀክት አመራር ድክመት ተጓትቶ ቆይቷል፡፡ ይሁን እንጂ በ2017 በጀት ዓመት በጠቅላይ ሚኒስትሩ ቀጥተኛ አመራር፣ አፈጻጸሙ ዝቅተኛ የነበረው ተቋራጭ ከፕሮጀክቱ እንዲወጣ ተደርጎ ሥራው ለሀገር በቀል ተቋራጭ ተሰጥቷል፡፡
የውጭ ከፍተኛ ባለሙያዎች ተጋብዘው የመሬት መንሸራተት ችግሩ በጥናት እንዲፈታ መደረጉ፣ እንዲሁም ሥራው በቀን እና በሌሊት ፈረቃ እንዲከናወን መወሰኑ ፕሮጀክቱን ከእንቅልፉ ቀስቅሶ ወደ ጤናማ እና ፈጣን የአፈጻጸም ምዕራፍ አሸጋግሮታል፡፡
በዚህም የግንባታው ወሳኝ ምዕራፍ የሆነው የወንዝ ቅልበሳ ሙሉ በሙሉ የተጠናቀቀ ሲሆን፣ ፕሮጀክቱ በቅርቡ ለፍሬ እንደሚበቃ ይጠበቃል፡፡
የመገጭ ግድብ ከግንባታ ባለፈ የኢትዮጵያውያን የልማት ፅናት ማሳያ ነው፡፡ አጠቃላይ የውኃ መያዝ አቅሙ 185 ሚሊዮን ኪዩቢክ ሜትር ሲሆን፣ ከዚህ ውስጥ 116 ሚሊዮን ኪዩቢክ ሜትር የሚሆነው ለመስኖ ልማት የሚውል ነው፡፡
ይህም 17 ሺህ ሔክታር መሬትን በመስኖ በማልማት የጎንደር ከተማን እንዲሁም የምሥራቅ እና የምዕራብ ደምቢያ አካባቢ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ ያደርጋል፡፡
ክልሉ ያለውን ሰፊ የውኃ እና የመሬት ሀብት አቀናጅቶ ለመጠቀም እየተገነቡ ካሉ ሰፋፊ የመስኖ አውታሮች አንዱ የሆነው ይህ ፕሮጀክት፣ የሀገራችን የግብርና ትራንስፎርሜሽን እና የምግብ ዋስትና ራዕይ በጉልህ የሚያሳካ የዘመን ትሩፋት ነው፡፡
ይህ የኢትዮጵያ የማይቆም የልማት እርምጃ እንደተለመደው የግብፅ ሚዲያዎችን ሰላም ነስቷል፡፡
የመገጭ ግድብ በጣና ሐይቅ ገባር ወንዝ ላይ የሚገነባ መካከለኛ ፕሮጀክት ቢሆንም፣ የግብፅ ሚዲያዎች ፕሮጀክቱን በተመለከተ ሰሞኑን እያስተጋቡት ያለው ጩኸት ሀገሪቱ ከያዘችው የቆየ እና ራስ ወዳድ የውኃ ፖሊሲ የሚመነጭ ነው፡፡
ግብፅ ኢትዮጵያ የውኃ ሀብቷን እንዳትጠቀም የማስፈራራት ፖሊሲን ብትከተልም፣ ኢትዮጵያ ግን ታላቁን የሕዳሴ ግድብ አጠናቅቃ ልማቷን የሚያፋጥኑ እንደ መገጭ ያሉ ግድቦችን መቀጠ "ኢትዮጵያ አትጨበጥም" የሚል ድንጋጤ ፈጥሮባቸዋል፡፡
ግብፅ አሁንም ጊዜ ያለፈባቸውን የቅኝ ግዛት ውሎች እያነሳች የትኛውም የኢትዮጵያ ልማት ግብርናዋን እንደሚጎዳ በማስመሰል ከእውነት የራቀ ኢ-ፍትሐዊ ትርክት ታራምዳለች፡፡
ኢትዮጵያ ግን ፍትሐዊና ምክንያታዊ የውኃ አጠቃቀም መርህን (CFA) በመከተል ሕዝቧን ለመመገብ የገዛ ሀብቷን የማልማት ተፈጥሯዊና ሕጋዊ መብቷን እያስከበረች ትገኛለች፡፡
ከዚህም ባሻገር እንደ መገጭ ባሉ የኢትዮጵያ ደጋማ ቦታዎች ግድብ መሥራት የውኃ ትነትን እጅግ የሚቀንስ መሆኑ የኢትዮጵያ ልማት ማንንም የማይጎዳ ለመሆኑ ሳይንሳዊ ማረጋገጫ ነው፡፡
እውነታው ኢትዮጵያ አሁን ያለችበት ምዕራፍ ከትላንቱ በእጅጉ የተለየ መሆኑ ነው፡፡ ሀገራችን የዜጎቿን ሕይወት ለመለወጥ እና ከድህነት ለመውጣት የምታደርገውን የልማት ጉዞ በማንኛውም የውጭ ኃይል እጅ ጥምዘዛ የማታቆምበት ታሪካዊ ከፍታ ላይ ትገኛለች፡፡
የመገጭ ግድብም ሆነ ሌሎች በሀገራችን እየተከናወኑ ያሉ የልማት ፕሮጀክቶች የዚሁ ሉዓላዊ መብት አካል ናቸው፡፡
ማንም ይጩህ ማን፣ ኢትዮጵያ በራሷ ሀብት፣ በራሷ አቅም እና በራሷ ጊዜ የጀመረቻቸውን የልማት ሥራዎች ከዳር በማድረስ ታሪኳን በአዲስ መልክ መጻፏን አጠናክራ ትቀጥላለች፡፡
መንግሥትም በቀጣይ የመገጭ ግድብ ቀሪ ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ በማጠናቀቅ፣ የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ሥራዎችን በማጠናከር እና በዓለም አቀፍ ደረጃ የዲፕሎማሲ ሥራውን በማስፋት የኢትዮጵያን ብልጽግና ያረጋግጣል፡፡
በለሚ ታደሰ
#ethiopia #ebc #megechdam #nile #development #amhararegion
****************
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን ጋር ባደረጉት ቆይታ በአማራ ክልል እየተከናወኑ ያሉ ታላላቅ የልማት ፕሮጀክቶችን በተመለከተ ሰፊ ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡
ከእነዚህ ሀገራዊ ፕሮጀክቶች መካከል የጎንደር ከተማ ነዋሪዎችን የረዥም ዘመን የመጠጥ ውኃ ጥያቄ የሚመልሰው እና ሰፊ የመስኖ ልማት አቅም ያለው የመገጭ ግድብ በግንባር ቀደምትነት ይጠቀሳል፡፡
ግንባታው በ2001 ዓ.ም. የተጀመረው ይህ ግድብ፣ ላለፉት 18 ዓመታት የመልካም አስተዳደር እና የፕሮጀክት አመራር ድክመት ተጓትቶ ቆይቷል፡፡ ይሁን እንጂ በ2017 በጀት ዓመት በጠቅላይ ሚኒስትሩ ቀጥተኛ አመራር፣ አፈጻጸሙ ዝቅተኛ የነበረው ተቋራጭ ከፕሮጀክቱ እንዲወጣ ተደርጎ ሥራው ለሀገር በቀል ተቋራጭ ተሰጥቷል፡፡
የውጭ ከፍተኛ ባለሙያዎች ተጋብዘው የመሬት መንሸራተት ችግሩ በጥናት እንዲፈታ መደረጉ፣ እንዲሁም ሥራው በቀን እና በሌሊት ፈረቃ እንዲከናወን መወሰኑ ፕሮጀክቱን ከእንቅልፉ ቀስቅሶ ወደ ጤናማ እና ፈጣን የአፈጻጸም ምዕራፍ አሸጋግሮታል፡፡
በዚህም የግንባታው ወሳኝ ምዕራፍ የሆነው የወንዝ ቅልበሳ ሙሉ በሙሉ የተጠናቀቀ ሲሆን፣ ፕሮጀክቱ በቅርቡ ለፍሬ እንደሚበቃ ይጠበቃል፡፡
የመገጭ ግድብ ከግንባታ ባለፈ የኢትዮጵያውያን የልማት ፅናት ማሳያ ነው፡፡ አጠቃላይ የውኃ መያዝ አቅሙ 185 ሚሊዮን ኪዩቢክ ሜትር ሲሆን፣ ከዚህ ውስጥ 116 ሚሊዮን ኪዩቢክ ሜትር የሚሆነው ለመስኖ ልማት የሚውል ነው፡፡
ይህም 17 ሺህ ሔክታር መሬትን በመስኖ በማልማት የጎንደር ከተማን እንዲሁም የምሥራቅ እና የምዕራብ ደምቢያ አካባቢ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ ያደርጋል፡፡
ክልሉ ያለውን ሰፊ የውኃ እና የመሬት ሀብት አቀናጅቶ ለመጠቀም እየተገነቡ ካሉ ሰፋፊ የመስኖ አውታሮች አንዱ የሆነው ይህ ፕሮጀክት፣ የሀገራችን የግብርና ትራንስፎርሜሽን እና የምግብ ዋስትና ራዕይ በጉልህ የሚያሳካ የዘመን ትሩፋት ነው፡፡
ይህ የኢትዮጵያ የማይቆም የልማት እርምጃ እንደተለመደው የግብፅ ሚዲያዎችን ሰላም ነስቷል፡፡
የመገጭ ግድብ በጣና ሐይቅ ገባር ወንዝ ላይ የሚገነባ መካከለኛ ፕሮጀክት ቢሆንም፣ የግብፅ ሚዲያዎች ፕሮጀክቱን በተመለከተ ሰሞኑን እያስተጋቡት ያለው ጩኸት ሀገሪቱ ከያዘችው የቆየ እና ራስ ወዳድ የውኃ ፖሊሲ የሚመነጭ ነው፡፡
ግብፅ ኢትዮጵያ የውኃ ሀብቷን እንዳትጠቀም የማስፈራራት ፖሊሲን ብትከተልም፣ ኢትዮጵያ ግን ታላቁን የሕዳሴ ግድብ አጠናቅቃ ልማቷን የሚያፋጥኑ እንደ መገጭ ያሉ ግድቦችን መቀጠ "ኢትዮጵያ አትጨበጥም" የሚል ድንጋጤ ፈጥሮባቸዋል፡፡
ግብፅ አሁንም ጊዜ ያለፈባቸውን የቅኝ ግዛት ውሎች እያነሳች የትኛውም የኢትዮጵያ ልማት ግብርናዋን እንደሚጎዳ በማስመሰል ከእውነት የራቀ ኢ-ፍትሐዊ ትርክት ታራምዳለች፡፡
ኢትዮጵያ ግን ፍትሐዊና ምክንያታዊ የውኃ አጠቃቀም መርህን (CFA) በመከተል ሕዝቧን ለመመገብ የገዛ ሀብቷን የማልማት ተፈጥሯዊና ሕጋዊ መብቷን እያስከበረች ትገኛለች፡፡
ከዚህም ባሻገር እንደ መገጭ ባሉ የኢትዮጵያ ደጋማ ቦታዎች ግድብ መሥራት የውኃ ትነትን እጅግ የሚቀንስ መሆኑ የኢትዮጵያ ልማት ማንንም የማይጎዳ ለመሆኑ ሳይንሳዊ ማረጋገጫ ነው፡፡
እውነታው ኢትዮጵያ አሁን ያለችበት ምዕራፍ ከትላንቱ በእጅጉ የተለየ መሆኑ ነው፡፡ ሀገራችን የዜጎቿን ሕይወት ለመለወጥ እና ከድህነት ለመውጣት የምታደርገውን የልማት ጉዞ በማንኛውም የውጭ ኃይል እጅ ጥምዘዛ የማታቆምበት ታሪካዊ ከፍታ ላይ ትገኛለች፡፡
የመገጭ ግድብም ሆነ ሌሎች በሀገራችን እየተከናወኑ ያሉ የልማት ፕሮጀክቶች የዚሁ ሉዓላዊ መብት አካል ናቸው፡፡
ማንም ይጩህ ማን፣ ኢትዮጵያ በራሷ ሀብት፣ በራሷ አቅም እና በራሷ ጊዜ የጀመረቻቸውን የልማት ሥራዎች ከዳር በማድረስ ታሪኳን በአዲስ መልክ መጻፏን አጠናክራ ትቀጥላለች፡፡
መንግሥትም በቀጣይ የመገጭ ግድብ ቀሪ ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ በማጠናቀቅ፣ የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ሥራዎችን በማጠናከር እና በዓለም አቀፍ ደረጃ የዲፕሎማሲ ሥራውን በማስፋት የኢትዮጵያን ብልጽግና ያረጋግጣል፡፡
በለሚ ታደሰ
#ethiopia #ebc #megechdam #nile #development #amhararegion
4 days ago
በአማራ ክልል በሚቀጥሉት 25 ዓመታት ከተሜነት በተሟላ ደረጃ ይስፋፋል - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር)
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአማራ ክልል በሚቀጥሉት 25 ዓመታት ከተሜነት በተሟላ ደረጃ ይስፋፋል አሉ፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሀገራዊ ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ጉዳዮች ዙሪያ ከአሚኮ ጋር ባደረጉት ቆይታ፥ በአማራ ክልል በገጠር ያለው ነዋሪ የመብራት፣ የውሃ፣ የጤና የተለያዩ ጥያቄዎች ምላሽ እንዲያገኝ የሚሰራ መሆኑን ጠቁመዋል።
በዚህም በክልሉ በሚቀጥሉት 25 ዓመታት ከተሜነት በተሟላ ደረጃ ይስፋፋል ብለዋል፡፡
በመስኖ፣ በቴክኖሎጂ፣ ምርታማነትን የማሳደግ ጉዳይ አሁን ካለው ጋር ለውድድር የሚበቃ ነው ብዬ አላስብም ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ አምራች ዘርፉ፣ ኢንዱስትሪው በብዙ ደረጃ ይቀየራል ሲሉ ጠቁመዋል።
የዲጂታል ኢኮኖሚ በኢትዮጵያ ውስጥ በስፋት እንደሚረጋገጥ አንስተዋል።
አሁን ያለው ትውልድ በከፋፋይ፣ በውሸት፣ መሰረት በሌለው ታሪክ ላይ ቆሞ የሚነታረክ መሆኑ አብቅቶ የሚጠቅመውንና የሚፈይደውን የሀገርን ጥቅም ማዕከል ያደረገውን ትርክት ገንብቶ ለጋራ ጥቅም መረባረብ እንዳለበትም አመልክተዋል።
አማራን ብቻ ሳይሆን አካባቢን የሚጠቅም ብልጽግና እናረጋግጣለን፤ ብልጽግናውንም የሚያስተዳድር ትውልድን አብረን እንፈጥራለን ብለዋል።
ይህ ጉዳይ የሁሉንም ርብርብ እንደሚጠይቅ ገልጸው፤ ይህ ትውልድ ስራውን ከሰራ መጪው ትውልድ የተሻለ ህይወት እንደሚኖረውና የአማራም ህዝብ ከዚህ እንደሚጠቀም ተስፋ አደርጋለሁ ነው ያሉት፡፡
FBC
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአማራ ክልል በሚቀጥሉት 25 ዓመታት ከተሜነት በተሟላ ደረጃ ይስፋፋል አሉ፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሀገራዊ ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ጉዳዮች ዙሪያ ከአሚኮ ጋር ባደረጉት ቆይታ፥ በአማራ ክልል በገጠር ያለው ነዋሪ የመብራት፣ የውሃ፣ የጤና የተለያዩ ጥያቄዎች ምላሽ እንዲያገኝ የሚሰራ መሆኑን ጠቁመዋል።
በዚህም በክልሉ በሚቀጥሉት 25 ዓመታት ከተሜነት በተሟላ ደረጃ ይስፋፋል ብለዋል፡፡
በመስኖ፣ በቴክኖሎጂ፣ ምርታማነትን የማሳደግ ጉዳይ አሁን ካለው ጋር ለውድድር የሚበቃ ነው ብዬ አላስብም ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ አምራች ዘርፉ፣ ኢንዱስትሪው በብዙ ደረጃ ይቀየራል ሲሉ ጠቁመዋል።
የዲጂታል ኢኮኖሚ በኢትዮጵያ ውስጥ በስፋት እንደሚረጋገጥ አንስተዋል።
አሁን ያለው ትውልድ በከፋፋይ፣ በውሸት፣ መሰረት በሌለው ታሪክ ላይ ቆሞ የሚነታረክ መሆኑ አብቅቶ የሚጠቅመውንና የሚፈይደውን የሀገርን ጥቅም ማዕከል ያደረገውን ትርክት ገንብቶ ለጋራ ጥቅም መረባረብ እንዳለበትም አመልክተዋል።
አማራን ብቻ ሳይሆን አካባቢን የሚጠቅም ብልጽግና እናረጋግጣለን፤ ብልጽግናውንም የሚያስተዳድር ትውልድን አብረን እንፈጥራለን ብለዋል።
ይህ ጉዳይ የሁሉንም ርብርብ እንደሚጠይቅ ገልጸው፤ ይህ ትውልድ ስራውን ከሰራ መጪው ትውልድ የተሻለ ህይወት እንደሚኖረውና የአማራም ህዝብ ከዚህ እንደሚጠቀም ተስፋ አደርጋለሁ ነው ያሉት፡፡
FBC
Comments