8 days ago
ካሜራ አንግተው በሜዳ የሚውሉት የሀገር ፕሬዚዳንት
#ethiopia | የቼክ ሪፐብሊክ ፕሬዚዳንት ፔትር ፓቬል ለየት ያለ የዕረፍት ጊዜ የማሳለፋቸው ነገር የብዙዎችን ቀልብ ስበው ከረሙ።
ፕሬዚዳንቱ የእረፍት ጊዜያቸውን የሚያሳልፉት በተለመዱት ብዙ ጠባቂዎች በተሰበሰቡበት ስፍራዎች ወይም በቅጡ በተዘጋጁ የመዝናኛ ቦታዎች ሳይሆን በሃንጋሪ ግራንድ ፕሪ የፎርሙላ 1 ውድድር ላይ በይፋዊ የፎቶግራፍ ጋዜጠኝነት ስራ ላይ በመሰማራት ነው።
ለሞተር ስፖርት ውድድሮች ካላቸው ጥልቅ ፍቅርና ዝንባሌ የተነሳ ፕሬዚዳንት ፓቬል ሙሉ በሙሉ የተረጋገጠ ሕጋዊ የሜዲያ ፈቃድ በማውጣት በውድድሩ ስፍራ እንደ ማንኛውም ሙያተኛ ካሜራቸውን አንግበው ሲሰሩ ይታያሉ።
ከፍተኛ የመንግሥት የሥልጣን ማዕረግ ቢኖራቸውም የሚወዱትን ስፖርት በቅርበት ለመከታተልና የፎቶግራፍ ጥበብ ፍላጎታቸውን ለማርካት ያሳዩት ትህትና በብዙዎች ዘንድ ትልቅ አድናቆትን አትርፎላቸዋል።
በያፌት ገ/ህይወት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#ethiopia | የቼክ ሪፐብሊክ ፕሬዚዳንት ፔትር ፓቬል ለየት ያለ የዕረፍት ጊዜ የማሳለፋቸው ነገር የብዙዎችን ቀልብ ስበው ከረሙ።
ፕሬዚዳንቱ የእረፍት ጊዜያቸውን የሚያሳልፉት በተለመዱት ብዙ ጠባቂዎች በተሰበሰቡበት ስፍራዎች ወይም በቅጡ በተዘጋጁ የመዝናኛ ቦታዎች ሳይሆን በሃንጋሪ ግራንድ ፕሪ የፎርሙላ 1 ውድድር ላይ በይፋዊ የፎቶግራፍ ጋዜጠኝነት ስራ ላይ በመሰማራት ነው።
ለሞተር ስፖርት ውድድሮች ካላቸው ጥልቅ ፍቅርና ዝንባሌ የተነሳ ፕሬዚዳንት ፓቬል ሙሉ በሙሉ የተረጋገጠ ሕጋዊ የሜዲያ ፈቃድ በማውጣት በውድድሩ ስፍራ እንደ ማንኛውም ሙያተኛ ካሜራቸውን አንግበው ሲሰሩ ይታያሉ።
ከፍተኛ የመንግሥት የሥልጣን ማዕረግ ቢኖራቸውም የሚወዱትን ስፖርት በቅርበት ለመከታተልና የፎቶግራፍ ጥበብ ፍላጎታቸውን ለማርካት ያሳዩት ትህትና በብዙዎች ዘንድ ትልቅ አድናቆትን አትርፎላቸዋል።
በያፌት ገ/ህይወት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
11 days ago
በህይወት እያሉ ተመሰገኑ
(በዕዝራ እጅጉ)
.የመዲናዋ ጤና ቢሮ ነፃ ህክምና እንዲያገኙ ወሰነ
#ethiopia | አንጋፋ የሚድያ ባለሙያዎች አዲስ አለም ሓድጉና በልሁ ተረፈ ዛሬ ጋቢ በተደረበላቸው ዕለት ደስታቸውን መቆጣጠር ተስኗቸው ነበር።
በኢትዮጵያ የሚድያ ታሪክ የማይረሳ አሻራ ያኖሩት እነዚህ ጉምቱ ባለሙያዎች ከ 35 አመት በላይ በትጋት ያገለገሉ ሲሆን በሙያ አጋሮቻቸው ተከበው አድናቆት ሲቸራቸው ውለዋል።
ቅዳሜ ሐምሌ 18 2018 ዓ.ም ከ 4 ሰዓት ጀምሮ በወመዘክር መርስኤሀዘን አዳራሽ በተደረገው መርሀ ግብር የሚድያ ባለሙያዎች እና ወዳጆቻቸው ተገኝተው እኛም አመስጋኞቻችሁ ነን በማለት ለመርሀ ግብሩ ድምቀት ሰጥተዋል።
ባለሙያዎቹን ለማመስገን ራሱን የቻለ ኮሚቴ የተዋቀረ ሲሆን ይህም ኮሚቴ ባለሙያዎቹ በዘለቄታዊነት የሚታገዙበት መንገድ ያመቻቸ ነው።
ለዝግጅቱ መሳካት በተከፈተው የwhat is up ገፅ ኮሚቴው ውስጥ ተግባራቸውን የተወጡት ጥላሁን ካሣ ፣ሀብታሙ ድረስ ፣ሰለሞን ሀይለኢየሱስ፣ዕዝራ እጅጉ (ተወዳጅ ሚድያ)፣ አለም ታደሰ፣ሠናይት ሀይሌ፣እሸቱ ገለቱ፣ ጌጡ ተመስገን እና ግደይ ገብረ ሲሆኑ እነርሱም በዕለቱ እንደተናገሩት ሥራው በአጭር ጊዜ ታስቦ ለስኬት መብቃቱ ደስ ያሰኛቸው መሆኑን ተናግረዋል።
ለአንጋፋ ባለሙያዎቹ የአዲስ አበባ ጤና ቢሮ ነፃ ህክምና የሚያገኙበት መንገድ ያመቻቸ ሲሆን ይህ የመረዳዳት ባህል ወደፊትም ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ ተነግሯል።
አዲስ አለም ሓድጉ በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን በትግርኛ ክፍል በኤዲተርነት እና በጋዜጠኝነት የሠራ ሲሆን ላለፉት 35 አመታትም ሙያውን ወዶና አክብሮ በመሥራት ይታወቃል።
የሚድያ ሰው በልሁ ተረፈ ደግሞ በኢትዮጵያ ሬድዮ ከሳይንስ ማህደር፣ ማንነት ሲፈተሽ እና ዝክረ ሰንበት በተባሉ ፕሮግራሞች ከ30 አመት በላይ የሠራ ሲሆን ሌሎችንም በማብቃት የማይዘነጋ አሻራ ለማኖር የቻለ ነው።
"ሰውን በሕይወት ሳለ እናመስግን "የሚል መርህ ያነገበው ይህ መሰናዶ የሚድያ ባለሙያዎችን በኑሯቸው የማገዝ ፣ በችግራቸው ጊዜ አብሯቸው የመሆን ግብ የሰነቀ ነው። እንዲህ አይነቱ ተግባር ወደፊትም ተጠናክሮ ይቀጥላል ተብሏል።
ሁለቱም ባለሙያዎች አገር የጣለችባቸውን አደራ የተወጡ ብርቱ ባለሙያዎች እንደነበሩ በዕለቱ ምስክርነት የሰጡ ባልደረቦቻቸው የተናገሩ ሲሆን የምስጋና ቀን መዘጋጀቱ አዲስ የሚመጣውንም ባለሙያ የሚያበረታታ ነው ሲሉ ሀሣብ ሰንዝረዋል።
በዕለቱ የሚድያ ሥራን ከ1950ዎቹ ጀምሮ ያስቃኘ አጭር የትዝታ ዘጋቢ ፊልም የቀረበ ሲሆን ተመስጋኞቹ ከዚህ ቀደም አየር ላይ ያዋሏቸው ሥራዎችም በዕለቱ ለታደሙት እንግዶች ቀርበዋል።
በባልደረቦቻቸው የምስጋና ዝግጅት የተደረገላቸው አዲስአለም ሓድጉና በልሁ ተረፈ እንደዛሬ ደስ ብሎንም አያውቅ ፣ ይህን መርሀ ግብር በተሳካ መንገድ ዕውን እንዲሆን የጣራችሁ ሁሉ ፈጣሪ መንገዳችሁን ያቃና ሲሉ መርቀዋል።
የአዘጋጅ ኮሚቴው አባል እሸቱ ገለቱ እንዳለው በኢትዮጵያ ሬድዮና ቴሌቪዥን የሚሠሩ ባልደረቦች የመጠያየቅ ባህልን ከጀመሩ ሁለት አመት እንደሆናቸው ጠቅሰው ይህ የምስጋና መርሀ ግብር የዚያ መጠያየቅ አካል እንደሆነ ጠቁሟል።
ባለሙያዎች ጡረታ ሲወጡ የሚደገፉበት፣ በተለይም በኢኮኖሚ እገዛ የሚያገኙበት ስልት መነደፍ እንዳለበትም ጋዜጠኛ እሸቱ ጥቆማ ሰጥቷል። በተጨማሪም የጤና ሁኔታቸውን፣ የሚከታተሉበት መንገድ መፈጠር እንዳለበትም ተናግሯል።
ከጡረታ በኃላ ምክር በመስጠት ባለሙያዎቹ ልምዳቸውን ማጋራት አለባቸውም ብሏል።ይህንኑ ትልቅ ርዕይ ለማሳካት መንግሥትና የሚመለከታቸው የሚድያ ማህበራት ሊተባበሩ ይገባልም ሲል ሀሣብ አንስቷል።
የእለቱን የምስጋና መሰናዶ እንዲሳካ አቶ ሠርፀፍሬ ስብሓት አዳራሽ በመስጠት ፣ ጋዜጠኛ ማህደረ ታሪኩ ፕሮጀክተር በመለገስ እንዲሁም አልፋ ውሃ፣ ለታዳሚዎች የመስተንግዶ ውሃ በማቅረብ መርሀ ግብሩ የተሳካ እንዲሆን አድርገዋል።
(በዕዝራ እጅጉ)
.የመዲናዋ ጤና ቢሮ ነፃ ህክምና እንዲያገኙ ወሰነ
#ethiopia | አንጋፋ የሚድያ ባለሙያዎች አዲስ አለም ሓድጉና በልሁ ተረፈ ዛሬ ጋቢ በተደረበላቸው ዕለት ደስታቸውን መቆጣጠር ተስኗቸው ነበር።
በኢትዮጵያ የሚድያ ታሪክ የማይረሳ አሻራ ያኖሩት እነዚህ ጉምቱ ባለሙያዎች ከ 35 አመት በላይ በትጋት ያገለገሉ ሲሆን በሙያ አጋሮቻቸው ተከበው አድናቆት ሲቸራቸው ውለዋል።
ቅዳሜ ሐምሌ 18 2018 ዓ.ም ከ 4 ሰዓት ጀምሮ በወመዘክር መርስኤሀዘን አዳራሽ በተደረገው መርሀ ግብር የሚድያ ባለሙያዎች እና ወዳጆቻቸው ተገኝተው እኛም አመስጋኞቻችሁ ነን በማለት ለመርሀ ግብሩ ድምቀት ሰጥተዋል።
ባለሙያዎቹን ለማመስገን ራሱን የቻለ ኮሚቴ የተዋቀረ ሲሆን ይህም ኮሚቴ ባለሙያዎቹ በዘለቄታዊነት የሚታገዙበት መንገድ ያመቻቸ ነው።
ለዝግጅቱ መሳካት በተከፈተው የwhat is up ገፅ ኮሚቴው ውስጥ ተግባራቸውን የተወጡት ጥላሁን ካሣ ፣ሀብታሙ ድረስ ፣ሰለሞን ሀይለኢየሱስ፣ዕዝራ እጅጉ (ተወዳጅ ሚድያ)፣ አለም ታደሰ፣ሠናይት ሀይሌ፣እሸቱ ገለቱ፣ ጌጡ ተመስገን እና ግደይ ገብረ ሲሆኑ እነርሱም በዕለቱ እንደተናገሩት ሥራው በአጭር ጊዜ ታስቦ ለስኬት መብቃቱ ደስ ያሰኛቸው መሆኑን ተናግረዋል።
ለአንጋፋ ባለሙያዎቹ የአዲስ አበባ ጤና ቢሮ ነፃ ህክምና የሚያገኙበት መንገድ ያመቻቸ ሲሆን ይህ የመረዳዳት ባህል ወደፊትም ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ ተነግሯል።
አዲስ አለም ሓድጉ በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን በትግርኛ ክፍል በኤዲተርነት እና በጋዜጠኝነት የሠራ ሲሆን ላለፉት 35 አመታትም ሙያውን ወዶና አክብሮ በመሥራት ይታወቃል።
የሚድያ ሰው በልሁ ተረፈ ደግሞ በኢትዮጵያ ሬድዮ ከሳይንስ ማህደር፣ ማንነት ሲፈተሽ እና ዝክረ ሰንበት በተባሉ ፕሮግራሞች ከ30 አመት በላይ የሠራ ሲሆን ሌሎችንም በማብቃት የማይዘነጋ አሻራ ለማኖር የቻለ ነው።
"ሰውን በሕይወት ሳለ እናመስግን "የሚል መርህ ያነገበው ይህ መሰናዶ የሚድያ ባለሙያዎችን በኑሯቸው የማገዝ ፣ በችግራቸው ጊዜ አብሯቸው የመሆን ግብ የሰነቀ ነው። እንዲህ አይነቱ ተግባር ወደፊትም ተጠናክሮ ይቀጥላል ተብሏል።
ሁለቱም ባለሙያዎች አገር የጣለችባቸውን አደራ የተወጡ ብርቱ ባለሙያዎች እንደነበሩ በዕለቱ ምስክርነት የሰጡ ባልደረቦቻቸው የተናገሩ ሲሆን የምስጋና ቀን መዘጋጀቱ አዲስ የሚመጣውንም ባለሙያ የሚያበረታታ ነው ሲሉ ሀሣብ ሰንዝረዋል።
በዕለቱ የሚድያ ሥራን ከ1950ዎቹ ጀምሮ ያስቃኘ አጭር የትዝታ ዘጋቢ ፊልም የቀረበ ሲሆን ተመስጋኞቹ ከዚህ ቀደም አየር ላይ ያዋሏቸው ሥራዎችም በዕለቱ ለታደሙት እንግዶች ቀርበዋል።
በባልደረቦቻቸው የምስጋና ዝግጅት የተደረገላቸው አዲስአለም ሓድጉና በልሁ ተረፈ እንደዛሬ ደስ ብሎንም አያውቅ ፣ ይህን መርሀ ግብር በተሳካ መንገድ ዕውን እንዲሆን የጣራችሁ ሁሉ ፈጣሪ መንገዳችሁን ያቃና ሲሉ መርቀዋል።
የአዘጋጅ ኮሚቴው አባል እሸቱ ገለቱ እንዳለው በኢትዮጵያ ሬድዮና ቴሌቪዥን የሚሠሩ ባልደረቦች የመጠያየቅ ባህልን ከጀመሩ ሁለት አመት እንደሆናቸው ጠቅሰው ይህ የምስጋና መርሀ ግብር የዚያ መጠያየቅ አካል እንደሆነ ጠቁሟል።
ባለሙያዎች ጡረታ ሲወጡ የሚደገፉበት፣ በተለይም በኢኮኖሚ እገዛ የሚያገኙበት ስልት መነደፍ እንዳለበትም ጋዜጠኛ እሸቱ ጥቆማ ሰጥቷል። በተጨማሪም የጤና ሁኔታቸውን፣ የሚከታተሉበት መንገድ መፈጠር እንዳለበትም ተናግሯል።
ከጡረታ በኃላ ምክር በመስጠት ባለሙያዎቹ ልምዳቸውን ማጋራት አለባቸውም ብሏል።ይህንኑ ትልቅ ርዕይ ለማሳካት መንግሥትና የሚመለከታቸው የሚድያ ማህበራት ሊተባበሩ ይገባልም ሲል ሀሣብ አንስቷል።
የእለቱን የምስጋና መሰናዶ እንዲሳካ አቶ ሠርፀፍሬ ስብሓት አዳራሽ በመስጠት ፣ ጋዜጠኛ ማህደረ ታሪኩ ፕሮጀክተር በመለገስ እንዲሁም አልፋ ውሃ፣ ለታዳሚዎች የመስተንግዶ ውሃ በማቅረብ መርሀ ግብሩ የተሳካ እንዲሆን አድርገዋል።
13 days ago
በህይወት ያለን እንመሰጋገን
አንጋፋ የሚድያ ባለሙያዎች አዲስአለምና በልሁ ሊመሰነጉ ነው
በኢትዮጵያ የሚድያ ታሪክ የማይረሳ አሻራ ያኖሩት አዲስ አለም ሓድጉና በልሁ ተረፈ የምስጋና መርሀ ግብር ሊደረግላቸው ነው።
ቅዳሜ ሐምሌ 18 2018 ዓ.ም በወመዘክር መርስኤሀዘን አዳራሽ በሚደረገው የምስጋና መርሀ ግብር የባለሙያዎቹ አድናቂዎች እና ወዳጆች ይታደማሉ።
አዲስ አለም ሓድጉ በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን በትግርኛ ክፍል በኤዲተርነት እና በጋዜጠኝነት የሠራ ሲሆን ላለፉት 35 አመታትም ሙያውን ወዶና አክብሮ በመሥራት ይታወቃል።
የሚድያ ሰው በልሁ ተረፈ ደግሞ በኢትዮጵያ ሬድዮ ከሳይንስ ማህደር፣ ማንነት ሲፈተሽ እና ዝክረ ሰንበት በተባሉ ፕሮግራሞች ከ30 አመት በላይ የሠራ ሲሆን ሌሎችንም በማብቃት የማይዘነጋ አሻራ ለማኖር የቻለ ነው።
ሰውን በሕይወት ሳለ እናመስግን የሚል መርህ ያነገበው ይህ መሰናዶ የሚድያ ባለሙያዎችን በኑሯቸው የማገዝ ፣ በችግራቸው ጊዜ አብሯቸው የመሆን ግብ የሰነቀ ነው። እንዲህ አይነቱ ባለሙያዎችን የማገዝ ተግባር ወደፊትም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ታውቋል።
ሁለቱም ባለሙያዎች አገር የጣለችባቸውን አደራ የተወጡ ብርቱ ባለሙያዎች ሲሆኑ ነገር ግን በኑሮ መደገፍ እና መመስገን ያለባቸው በመሆኑ ለዚህ መርሀ ግብር ኮሚቴ ተዋቅሮ እየተሠራ እንደሆነ ለማወቅ ተችሏል።
አንጋፋ የሚድያ ባለሙያዎች አዲስአለምና በልሁ ሊመሰነጉ ነው
በኢትዮጵያ የሚድያ ታሪክ የማይረሳ አሻራ ያኖሩት አዲስ አለም ሓድጉና በልሁ ተረፈ የምስጋና መርሀ ግብር ሊደረግላቸው ነው።
ቅዳሜ ሐምሌ 18 2018 ዓ.ም በወመዘክር መርስኤሀዘን አዳራሽ በሚደረገው የምስጋና መርሀ ግብር የባለሙያዎቹ አድናቂዎች እና ወዳጆች ይታደማሉ።
አዲስ አለም ሓድጉ በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን በትግርኛ ክፍል በኤዲተርነት እና በጋዜጠኝነት የሠራ ሲሆን ላለፉት 35 አመታትም ሙያውን ወዶና አክብሮ በመሥራት ይታወቃል።
የሚድያ ሰው በልሁ ተረፈ ደግሞ በኢትዮጵያ ሬድዮ ከሳይንስ ማህደር፣ ማንነት ሲፈተሽ እና ዝክረ ሰንበት በተባሉ ፕሮግራሞች ከ30 አመት በላይ የሠራ ሲሆን ሌሎችንም በማብቃት የማይዘነጋ አሻራ ለማኖር የቻለ ነው።
ሰውን በሕይወት ሳለ እናመስግን የሚል መርህ ያነገበው ይህ መሰናዶ የሚድያ ባለሙያዎችን በኑሯቸው የማገዝ ፣ በችግራቸው ጊዜ አብሯቸው የመሆን ግብ የሰነቀ ነው። እንዲህ አይነቱ ባለሙያዎችን የማገዝ ተግባር ወደፊትም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ታውቋል።
ሁለቱም ባለሙያዎች አገር የጣለችባቸውን አደራ የተወጡ ብርቱ ባለሙያዎች ሲሆኑ ነገር ግን በኑሮ መደገፍ እና መመስገን ያለባቸው በመሆኑ ለዚህ መርሀ ግብር ኮሚቴ ተዋቅሮ እየተሠራ እንደሆነ ለማወቅ ተችሏል።
20 days ago
የአንጋፋው ጋዜጠኛና የኮሙኒኬሽን ባለሙያ እሸቱ ዱብ
የቀብር ሥነ ሥርዓት ዛሬ ተፈጽሟል
#ethiopia | በጋዜጠኝነት፣ በኮርፖሬት ኮሙኒኬሽን፣ በቢዝነስ ስትራቴጂ፣ በሥነ ጽሑፍና በፊልም ዘርፍ የሚታወቁት አንጋፋው ጋዜጠኛ እሸቱ ዱብ በ50 ዓመታቸው አርፈዋል።
እሸቱ ዱብ ሐምሌ 7 ቀን 2018 ዓ.ም. በሕይወት ማለፋቸው የተነገረ ሲሆን፣ የቀብር ሥነ ሥርዓታቸውም ዛሬ ሐምሌ 10 ቀን 2018 ዓ.ም. በጣፎ ተክለሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን ተፈጽሟል።
ከ30 ዓመታት በላይ በሚዲያና ኮሙኒኬሽን ዘርፍ ያገለገሉት እሸቱ፣ በ1987 ዓ.ም. ፋና ሬዲዮ ሲመሠረት ከመጀመሪያዎቹ ባልደረቦች አንዱ በመሆን የመዝናኛ ክፍሉን በመምራት ዘርፉ ላይ የማይረሳ አሻራ አሳርፈዋል።
ከጋዜጠኝነት ባሻገር በኮርፖሬት ኮሙኒኬሽን፣ ብራንዲንግ፣ ማርኬቲንግ እና የቢዝነስ ስትራቴጂ ዘርፎች በሰፊው ሠርተዋል።
በCRDA የኮርፖሬት ኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር፣ በዋፋ ማርኬቲንግ የብራንዲንግና መልቲሚዲያ ፕሮዳክሽን ኃላፊ እንዲሁም በተለያዩ ተቋማት አማካሪና አሠልጣኝ ሆነው አገልግለዋል።
በሥነ ጽሑፍ ዘርፍም "ቀይ ልበሽ" የግጥም መድበል እና "የቅርብ ሩቅ" የተሰኘ ተውኔትን ጨምሮ በርካታ ሥራዎችን አበርክተዋል።
በኢኮኖሚ፣ በፖሊሲና በማህበራዊ ጉዳዮች ላይ የሚያተኩሩ ጽሑፎቻቸውም በስፋት ተነብበዋል።
በእውቀታቸው፣ በትህትናቸው፣ በሙያዊ ብቃታቸው እና ወጣት ጋዜጠኞችን በማብቃት በኢትዮጵያ ሚዲያ ዘርፍ ዘላቂ አሻራ አስቀምጠው አልፈዋል።
ነፍሳቸውን ይማር።
የቀብር ሥነ ሥርዓት ዛሬ ተፈጽሟል
#ethiopia | በጋዜጠኝነት፣ በኮርፖሬት ኮሙኒኬሽን፣ በቢዝነስ ስትራቴጂ፣ በሥነ ጽሑፍና በፊልም ዘርፍ የሚታወቁት አንጋፋው ጋዜጠኛ እሸቱ ዱብ በ50 ዓመታቸው አርፈዋል።
እሸቱ ዱብ ሐምሌ 7 ቀን 2018 ዓ.ም. በሕይወት ማለፋቸው የተነገረ ሲሆን፣ የቀብር ሥነ ሥርዓታቸውም ዛሬ ሐምሌ 10 ቀን 2018 ዓ.ም. በጣፎ ተክለሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን ተፈጽሟል።
ከ30 ዓመታት በላይ በሚዲያና ኮሙኒኬሽን ዘርፍ ያገለገሉት እሸቱ፣ በ1987 ዓ.ም. ፋና ሬዲዮ ሲመሠረት ከመጀመሪያዎቹ ባልደረቦች አንዱ በመሆን የመዝናኛ ክፍሉን በመምራት ዘርፉ ላይ የማይረሳ አሻራ አሳርፈዋል።
ከጋዜጠኝነት ባሻገር በኮርፖሬት ኮሙኒኬሽን፣ ብራንዲንግ፣ ማርኬቲንግ እና የቢዝነስ ስትራቴጂ ዘርፎች በሰፊው ሠርተዋል።
በCRDA የኮርፖሬት ኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር፣ በዋፋ ማርኬቲንግ የብራንዲንግና መልቲሚዲያ ፕሮዳክሽን ኃላፊ እንዲሁም በተለያዩ ተቋማት አማካሪና አሠልጣኝ ሆነው አገልግለዋል።
በሥነ ጽሑፍ ዘርፍም "ቀይ ልበሽ" የግጥም መድበል እና "የቅርብ ሩቅ" የተሰኘ ተውኔትን ጨምሮ በርካታ ሥራዎችን አበርክተዋል።
በኢኮኖሚ፣ በፖሊሲና በማህበራዊ ጉዳዮች ላይ የሚያተኩሩ ጽሑፎቻቸውም በስፋት ተነብበዋል።
በእውቀታቸው፣ በትህትናቸው፣ በሙያዊ ብቃታቸው እና ወጣት ጋዜጠኞችን በማብቃት በኢትዮጵያ ሚዲያ ዘርፍ ዘላቂ አሻራ አስቀምጠው አልፈዋል።
ነፍሳቸውን ይማር።
21 days ago
የ"ሸገሩ"፣ "የእነሆ መቆያው" እሸቴ አሰፋ!
#ethiopia | ባለፈው ሳምንት "እነሆ መቆያ" የተሰኘ መጽሐፉን ለንባብ ያበቃው፣ አንጋፋውና ስመ-ጥሩ ጋዜጠኛ እሸቴ አሰፋ (እሸቴ ከጃንሜዳ) ሐምሌ 19 ቀን 1953 ዓ.ም በሰሜን ሸዋ መንዝና ግሼ አውራጃ ተወለደ።
የአንደኛ ደረጃ ትምህርቱን በተወለደበት አካባቢ ራቤል የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤት ያጠናቀቀ ሲሆን፣ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱን ደግሞ በመሐል ሜዳ፣ በሆለታና በአቃቂ ተማሪ ቤቶች ተከታትሏል።
ገና በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት እያለ በሚኒ-ሚዲያ በመሳተፍ የጋዜጠኝነት ፍቅሩን ያሳየው እሸቴ፣ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በቋንቋና ሥነ-ጽሑፍ የመጀመሪያ ዲግሪውን አግኝቷል።
ለመጀመሪያ ጊዜ ጽሑፉ የታተመለት በአዲስ ዘመን ጋዜጣ "አድማስ" አምድ ላይ ነበር ይላል - ለዚህ ጽሑፍ ዋነኛ ምንጭ አድርገን የተጠቀምነው የ"ተወዳጅ ሚዲያ" መረጃ።
በተለይም "የካቲት" መጽሔት ላይ እንደ ጳውሎስ ኞኞ፣ ስብሐት ገብረእግዚአብሔር፣ ብርሃኑ ዘርይሁን፣ ወጋየሁ ንጋቱ፣ ይድነቃቸው ተሰማና ፕሮፌሰር አስራት ወልደየስ ያሉ ታላላቅ ሰዎችን ታሪክ በጥናት አስደግፎ በማቅረብ የአንባቢን ልብ መግዛት ችሏል።
በተለያዩ ዘርፎች ብዙ ውለታ የዋሉ ታላላቅ የሀገራችንን ሰብዕናዎችንም 'ቃለ-መጠይቅ' (Interview) አድርጓል።
በዚህ የጋዜጠኝነት ጉዞው ውስጥ የአጻጻፍና የጋዜጠኝነት ሙያዊ ዕውቀት የሰጡትንና እንደ መምህር የሚያያቸውን የመጽሔቷን ዋና አዘጋጅ አቶ ጸጋዬ ኃይሉ ተፈራን ምንጊዜም በታላቅ አክብሮት ያስታውሳል።
በአንድ ጊዜ በበርካታ ሚዲያዎች ላይ የመሥራት ልዩ ታታሪነት የነበረው እሸቴ፣ ከ1978 ዓ.ም ጀምሮ ለአምስት ዓመታት ያህል በለገዳዲ ሬዲዮ "የእሁድ ለአንዳፍታ" ፕሮግራም ላይ "እሸቴ ከጃንሜዳ" በሚል ስያሜ የገጠሪቱን ኢትዮጵያ ባህልና ውሎ የሚያሳዩ ማራኪ የሥነ-ቃል ስብስቦችን በራሱ አንደበት እያነበበ ለአድማጭ ያቀርብ ነበር።
በተያያዥነትም ከ1979 ዓ.ም ጀምሮ በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን በፍሪላንስ ጋዜጠኛነት በመቀጠር፣ በተለይ ታሪካዊና ተፈጥሯዊ አካባቢዎች ላይ ያተኮሩ የተለያዩ ባለ አንድ ሰዓት ዘጋቢ ፊልሞችን (ዶክመንተሪዎችን) አዘጋጅቷል።
ከእነዚህም መካከል ስለ ጣና ሐይቅ አድባራት የሠራውና አዲስ አበባ 100ኛ ዓመቷን ስታከብር ያቀረበው ባለ አንድ ሰዓት ተኩል ልዩ ፕሮግራም ተጠቃሽ ናቸው።
በ1987 ዓ.ም "ሪፖርተር" ጋዜጣ ሲመሠረት ከዋና መሥራቾቹ አንዱ የነበረ ሲሆን፣ ከ1989 ዓ.ም ጀምሮ ደግሞ የ"ሪፖርተር" ጋዜጣና መጽሔት ምክትል ዋና አዘጋጅና ዋና አዘጋጅ በመሆን ሙያዊና እውነተኛ መረጃ ላይ የተመሠረተ ጋዜጠኝነት እንዲሰፍን ከፍተኛ አስተዋጽኦ አበርክቷል።
ላለፉት አስራ አምስት ዓመታት ደግሞ በሸገር 102.1 ኤፍ ኤም ሬዲዮ በቅዳሜው "እነሆ መቆያ" መሰናዶው የዓለም መሪዎችን፣ ታዋቂ ሰዎችንና ታላላቅ የስለላ ተቋማትን፣ ታሪካዊ ክስተቶችን እና ሌሎችንም ጉዳዮች በበቂ ንባብና ማስረጃ አደራጅቶ በማቅረብ ከፍተኛ ተወዳጅነትን አትርፏል።
በአሁኑ ወቅትም በሸገር fm 102.1 ሬዲዮ ጣቢያ በዋና አዘጋጅነት እያገለገለ ይገኛል። ጋዜጠኛ እሸቴ አሰፋ ባለትዳርና የሁለት ልጆች አባት ነው።
ስለራሱ በአንደበቱ ከማውራት ይልቅ በሥራው መናገርን የሚመርጠው ይህ በሳል ጋዜጠኛ፣ ባለፉት ሠላሳ ዓመታት በሀገሪቱ ሚዲያ ታሪክ ውስጥ የራሱን የማይረሳ ደማቅ አሻራ አስቀምጧል። እናመሰግናለን፤ እሼ!
#ወይ_አዲስ_አበባ_on_Sheger_fm_102 .1 #sheger_fm_102 .1 #zefenenazemen #jafarbooks #radio #አዲስ_አበባ
#ethiopia | ባለፈው ሳምንት "እነሆ መቆያ" የተሰኘ መጽሐፉን ለንባብ ያበቃው፣ አንጋፋውና ስመ-ጥሩ ጋዜጠኛ እሸቴ አሰፋ (እሸቴ ከጃንሜዳ) ሐምሌ 19 ቀን 1953 ዓ.ም በሰሜን ሸዋ መንዝና ግሼ አውራጃ ተወለደ።
የአንደኛ ደረጃ ትምህርቱን በተወለደበት አካባቢ ራቤል የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤት ያጠናቀቀ ሲሆን፣ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱን ደግሞ በመሐል ሜዳ፣ በሆለታና በአቃቂ ተማሪ ቤቶች ተከታትሏል።
ገና በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት እያለ በሚኒ-ሚዲያ በመሳተፍ የጋዜጠኝነት ፍቅሩን ያሳየው እሸቴ፣ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በቋንቋና ሥነ-ጽሑፍ የመጀመሪያ ዲግሪውን አግኝቷል።
ለመጀመሪያ ጊዜ ጽሑፉ የታተመለት በአዲስ ዘመን ጋዜጣ "አድማስ" አምድ ላይ ነበር ይላል - ለዚህ ጽሑፍ ዋነኛ ምንጭ አድርገን የተጠቀምነው የ"ተወዳጅ ሚዲያ" መረጃ።
በተለይም "የካቲት" መጽሔት ላይ እንደ ጳውሎስ ኞኞ፣ ስብሐት ገብረእግዚአብሔር፣ ብርሃኑ ዘርይሁን፣ ወጋየሁ ንጋቱ፣ ይድነቃቸው ተሰማና ፕሮፌሰር አስራት ወልደየስ ያሉ ታላላቅ ሰዎችን ታሪክ በጥናት አስደግፎ በማቅረብ የአንባቢን ልብ መግዛት ችሏል።
በተለያዩ ዘርፎች ብዙ ውለታ የዋሉ ታላላቅ የሀገራችንን ሰብዕናዎችንም 'ቃለ-መጠይቅ' (Interview) አድርጓል።
በዚህ የጋዜጠኝነት ጉዞው ውስጥ የአጻጻፍና የጋዜጠኝነት ሙያዊ ዕውቀት የሰጡትንና እንደ መምህር የሚያያቸውን የመጽሔቷን ዋና አዘጋጅ አቶ ጸጋዬ ኃይሉ ተፈራን ምንጊዜም በታላቅ አክብሮት ያስታውሳል።
በአንድ ጊዜ በበርካታ ሚዲያዎች ላይ የመሥራት ልዩ ታታሪነት የነበረው እሸቴ፣ ከ1978 ዓ.ም ጀምሮ ለአምስት ዓመታት ያህል በለገዳዲ ሬዲዮ "የእሁድ ለአንዳፍታ" ፕሮግራም ላይ "እሸቴ ከጃንሜዳ" በሚል ስያሜ የገጠሪቱን ኢትዮጵያ ባህልና ውሎ የሚያሳዩ ማራኪ የሥነ-ቃል ስብስቦችን በራሱ አንደበት እያነበበ ለአድማጭ ያቀርብ ነበር።
በተያያዥነትም ከ1979 ዓ.ም ጀምሮ በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን በፍሪላንስ ጋዜጠኛነት በመቀጠር፣ በተለይ ታሪካዊና ተፈጥሯዊ አካባቢዎች ላይ ያተኮሩ የተለያዩ ባለ አንድ ሰዓት ዘጋቢ ፊልሞችን (ዶክመንተሪዎችን) አዘጋጅቷል።
ከእነዚህም መካከል ስለ ጣና ሐይቅ አድባራት የሠራውና አዲስ አበባ 100ኛ ዓመቷን ስታከብር ያቀረበው ባለ አንድ ሰዓት ተኩል ልዩ ፕሮግራም ተጠቃሽ ናቸው።
በ1987 ዓ.ም "ሪፖርተር" ጋዜጣ ሲመሠረት ከዋና መሥራቾቹ አንዱ የነበረ ሲሆን፣ ከ1989 ዓ.ም ጀምሮ ደግሞ የ"ሪፖርተር" ጋዜጣና መጽሔት ምክትል ዋና አዘጋጅና ዋና አዘጋጅ በመሆን ሙያዊና እውነተኛ መረጃ ላይ የተመሠረተ ጋዜጠኝነት እንዲሰፍን ከፍተኛ አስተዋጽኦ አበርክቷል።
ላለፉት አስራ አምስት ዓመታት ደግሞ በሸገር 102.1 ኤፍ ኤም ሬዲዮ በቅዳሜው "እነሆ መቆያ" መሰናዶው የዓለም መሪዎችን፣ ታዋቂ ሰዎችንና ታላላቅ የስለላ ተቋማትን፣ ታሪካዊ ክስተቶችን እና ሌሎችንም ጉዳዮች በበቂ ንባብና ማስረጃ አደራጅቶ በማቅረብ ከፍተኛ ተወዳጅነትን አትርፏል።
በአሁኑ ወቅትም በሸገር fm 102.1 ሬዲዮ ጣቢያ በዋና አዘጋጅነት እያገለገለ ይገኛል። ጋዜጠኛ እሸቴ አሰፋ ባለትዳርና የሁለት ልጆች አባት ነው።
ስለራሱ በአንደበቱ ከማውራት ይልቅ በሥራው መናገርን የሚመርጠው ይህ በሳል ጋዜጠኛ፣ ባለፉት ሠላሳ ዓመታት በሀገሪቱ ሚዲያ ታሪክ ውስጥ የራሱን የማይረሳ ደማቅ አሻራ አስቀምጧል። እናመሰግናለን፤ እሼ!
#ወይ_አዲስ_አበባ_on_Sheger_fm_102 .1 #sheger_fm_102 .1 #zefenenazemen #jafarbooks #radio #አዲስ_አበባ
24 days ago
መገናኛ ብዙሃን ብሔራዊ ጥቅም በማስጠበቅ ላይ ሊሰሩ ይገባል - መኩሪያ መካሻ (ረ/ፕ)
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 5፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) መገናኛ ብዙሃን በኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም ላይ ትኩረት አድርጎ መሥራት ይጠበቅበታል አሉ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጋዜጠኝነት እና ኮሙኒኬሽን መምህር መኩሪያ መካሻ (ረ/ፕ)።
መኩሪያ መካሻ (ረ/ፕ) ከፋና ፖድካስት ጋር ባደረጉት ቆይታ እንደገለጹት፥ ጋዜጠኞች የሀገርን ሉዓላዊነትና ክብር በሚያስጠብቁ ብሔራዊ ጥቅሞች ላይ በመሥራት ሚናቸውን ሊወጡ ይገባል።
የሀገራችን መገናኛ ብዙሃን በቀጣናው ተፅዕኖ ፈጣሪ መሆን አለባቸው ያሉት መምህሩ፥ የሀገርን ጥቅም በማስከበር ረገድ በጂኦፖለቲካዊ ጉዳዮች ገንቢ ሚናን መጫወት አስፈላጊ መሆኑን አስገንዝበዋል።
ማንነትና ታሪክን ለመግለፅ ብሎም ተፅዕኖ ለመፍጠር መገናኛ ብዙሃን ትልቅ አቅም እንዳላቸው ገልጸው፥ ገዢ ትርክት በማስረፅና ልዕለ ኃያል ሀገር በመገንባት ላይ ትኩረት አድርጎ መሥራት እንደሚገባ መክረዋል።
ይህ ወቅት ዲጂታል ሚዲያው ተጽዕኖ እያየለ የመጣበት ጊዜ በመሆኑ ኅብረተሰቡ እውነተኛውን መረጃ ለይቶ መጠቀም እንዲችል መሠረታዊ ትምህርት እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል።
ለመገናኛ ብዙሃን ውጤታማነት ፈጠራ ወሳኝ መሆኑን የገለጹ ሲሆን፥ የጋዜጠኝነት ስራ ተግባርን ያስቀድማል ሲሉም አብራርተዋል።
በሠራዊት ሸሎ
በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጋዜጠኝነት እና ኮሙኒኬሽን ትምህርት ከፍል መምህር መኩሪያ መካሻ (ረ/ፕ) ከፋና ፖድካስት ጋር ያደረጉትን ቆይታ ለመከታተል ማስፈንጠሪያውን ይጫኑ
https://youtube.com/watch?...
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 5፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) መገናኛ ብዙሃን በኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም ላይ ትኩረት አድርጎ መሥራት ይጠበቅበታል አሉ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጋዜጠኝነት እና ኮሙኒኬሽን መምህር መኩሪያ መካሻ (ረ/ፕ)።
መኩሪያ መካሻ (ረ/ፕ) ከፋና ፖድካስት ጋር ባደረጉት ቆይታ እንደገለጹት፥ ጋዜጠኞች የሀገርን ሉዓላዊነትና ክብር በሚያስጠብቁ ብሔራዊ ጥቅሞች ላይ በመሥራት ሚናቸውን ሊወጡ ይገባል።
የሀገራችን መገናኛ ብዙሃን በቀጣናው ተፅዕኖ ፈጣሪ መሆን አለባቸው ያሉት መምህሩ፥ የሀገርን ጥቅም በማስከበር ረገድ በጂኦፖለቲካዊ ጉዳዮች ገንቢ ሚናን መጫወት አስፈላጊ መሆኑን አስገንዝበዋል።
ማንነትና ታሪክን ለመግለፅ ብሎም ተፅዕኖ ለመፍጠር መገናኛ ብዙሃን ትልቅ አቅም እንዳላቸው ገልጸው፥ ገዢ ትርክት በማስረፅና ልዕለ ኃያል ሀገር በመገንባት ላይ ትኩረት አድርጎ መሥራት እንደሚገባ መክረዋል።
ይህ ወቅት ዲጂታል ሚዲያው ተጽዕኖ እያየለ የመጣበት ጊዜ በመሆኑ ኅብረተሰቡ እውነተኛውን መረጃ ለይቶ መጠቀም እንዲችል መሠረታዊ ትምህርት እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል።
ለመገናኛ ብዙሃን ውጤታማነት ፈጠራ ወሳኝ መሆኑን የገለጹ ሲሆን፥ የጋዜጠኝነት ስራ ተግባርን ያስቀድማል ሲሉም አብራርተዋል።
በሠራዊት ሸሎ
በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጋዜጠኝነት እና ኮሙኒኬሽን ትምህርት ከፍል መምህር መኩሪያ መካሻ (ረ/ፕ) ከፋና ፖድካስት ጋር ያደረጉትን ቆይታ ለመከታተል ማስፈንጠሪያውን ይጫኑ
https://youtube.com/watch?...
Sponsored by
Surafel
24 days ago
እውነትን መናገር አንዱ እሴት ነው -የጋዜጠኝነት እና ኮሙኒኬሽን መምህር መኩሪያ መካሻ (ረ/ፕ) ጋር የተደረገ ቆይታ ክፍል 2
ዛሬ 8፡00 በፋና ፖድካስት ይጠብቁን
#ለሀገር #ፖድካስት #ፋናፖድካስት #ፋናሚዲያኮርፖሬሽን #fanapodcast #fanadigitalmedia #fanamediacorporation #poodkaastiifaanaa #fanadigitalmedia #فا
26 days ago
እውነትን መናገር አንዱ እሴት ነው -የጋዜጠኝነት እና ኮሙኒኬሽን መምህር መኩሪያ መካሻ (ረ/ፕ) ጋር የተደረገ ቆይታ ክፍል 2
እሁድ 8፡00 በፋና ፖድካስት ይጠብቁን
#ለሀገር #ፖድካስት #ፋናፖድካስት #ፋናሚዲያኮርፖሬሽን #fanapodcast #fanadigitalmedia #fanamediacorporation #poodkaastiifaanaa #fanadigitalmedia #فا
27 days ago
በዊልቼር ሆኖ የዓለምን እግር ኳስ ኮከቦች ያነጋገረው ጋዜጠኛ – ማኑ ጉቲዬሬዝ
#ethiopia | ማኑ ጉቲዬሬዝ (Manu Gutiérrez) ገለልተኛ የቬንዙዌላ ስፖርት ጋዜጠኛና የMVP Sports መስራች ነው። በአሁኑ ወቅት የESPN ይፋዊ ዘጋቢ ወይም ቋሚ የሠራተኛ አባል ባይሆንም፣ በ2026 የፊፋ ዓለም ዋንጫ ባሳየው ቁርጠኝነት፣ ሙያዊ ሽፋን እና ከዓለም አቀፍ የእግር ኳስ ኮከቦች ጋር ባደረጋቸው ልዩ ቃለመጠይቆች ከፍተኛ ዓለም አቀፍ ትኩረትን ማግኘት ችሏል።
ጉቲዬሬዝ በCerebral Palsy የተነሳ የአካል ጉዳት ያለበት ሲሆን፣ በዊልቼር ተንቀሳቃሽ ነው። ይህ ግን የጋዜጠኝነት ሕልሙን ከማሳካት አላገደውም፤ በተቃራኒው በውድድሩ ላይ ካሉት እጅግ ልብን ከሚነኩ እና አነሳሽ ታሪኮች መካከል አንዱ ሆኗል።
ተወዳጅነትን ያተረፉለት አጋጣሚዎች
• የጁድ ቤሊንግሃም ልብ የነካ ቅጽበት፦ የእንግሊዙ ኮከብ ጁድ ቤሊንግሃም በሚክስድ ዞን ውስጥ ማኑን ሲያይ ቆሞ በማነጋገር፣ ለቬንዙዌላ ሕዝብ በስፓንኛ ቋንቋ ልባዊ መልእክት አስተላልፏል። ይህ ቅጽበት በማህበራዊ ሚዲያ በሚሊዮኖች የተመለከተ ሲሆን፣ ማኑንም ለዓለም ያስተዋወቀ አጋጣሚ ሆኗል።
• ከሊዮኔል ሜሲ ጋር የተደረገው የሕልም ቃለመጠይቅ፦ ማኑ የዓለም ዋንጫውን እንደ ገለልተኛ ጋዜጠኛ ለመዘገብ የሚያስችለውን የሚዲያ ፈቃድ ካገኘ በኋላ፣ ከአርጀንቲናው ካፒቴን ሊዮኔል ሜሲ ጋር ፊት ለፊት ቃለመጠይቅ በማድረግ የረጅም ዘመን ሕልሙን እውን አድርጓል።
የማኑ ጉቲዬሬዝ ታሪክ የአካል ጉዳት ሕልምን ሊገድብ እንደማይችል የሚያሳይ ጠንካራ ምሳሌ ሆኗል። በጽናት፣ በትጋትና በሙያዊ ቁርጠኝነት ከዓለም ታላላቅ የእግር ኳስ ኮከቦች ጋር በመገናኘት ለብዙ ሰዎች ተስፋና መነሳሳትን አስተላልፏል።
በእስከዳር ይኩኑአምላክ
#ethiopia | ማኑ ጉቲዬሬዝ (Manu Gutiérrez) ገለልተኛ የቬንዙዌላ ስፖርት ጋዜጠኛና የMVP Sports መስራች ነው። በአሁኑ ወቅት የESPN ይፋዊ ዘጋቢ ወይም ቋሚ የሠራተኛ አባል ባይሆንም፣ በ2026 የፊፋ ዓለም ዋንጫ ባሳየው ቁርጠኝነት፣ ሙያዊ ሽፋን እና ከዓለም አቀፍ የእግር ኳስ ኮከቦች ጋር ባደረጋቸው ልዩ ቃለመጠይቆች ከፍተኛ ዓለም አቀፍ ትኩረትን ማግኘት ችሏል።
ጉቲዬሬዝ በCerebral Palsy የተነሳ የአካል ጉዳት ያለበት ሲሆን፣ በዊልቼር ተንቀሳቃሽ ነው። ይህ ግን የጋዜጠኝነት ሕልሙን ከማሳካት አላገደውም፤ በተቃራኒው በውድድሩ ላይ ካሉት እጅግ ልብን ከሚነኩ እና አነሳሽ ታሪኮች መካከል አንዱ ሆኗል።
ተወዳጅነትን ያተረፉለት አጋጣሚዎች
• የጁድ ቤሊንግሃም ልብ የነካ ቅጽበት፦ የእንግሊዙ ኮከብ ጁድ ቤሊንግሃም በሚክስድ ዞን ውስጥ ማኑን ሲያይ ቆሞ በማነጋገር፣ ለቬንዙዌላ ሕዝብ በስፓንኛ ቋንቋ ልባዊ መልእክት አስተላልፏል። ይህ ቅጽበት በማህበራዊ ሚዲያ በሚሊዮኖች የተመለከተ ሲሆን፣ ማኑንም ለዓለም ያስተዋወቀ አጋጣሚ ሆኗል።
• ከሊዮኔል ሜሲ ጋር የተደረገው የሕልም ቃለመጠይቅ፦ ማኑ የዓለም ዋንጫውን እንደ ገለልተኛ ጋዜጠኛ ለመዘገብ የሚያስችለውን የሚዲያ ፈቃድ ካገኘ በኋላ፣ ከአርጀንቲናው ካፒቴን ሊዮኔል ሜሲ ጋር ፊት ለፊት ቃለመጠይቅ በማድረግ የረጅም ዘመን ሕልሙን እውን አድርጓል።
የማኑ ጉቲዬሬዝ ታሪክ የአካል ጉዳት ሕልምን ሊገድብ እንደማይችል የሚያሳይ ጠንካራ ምሳሌ ሆኗል። በጽናት፣ በትጋትና በሙያዊ ቁርጠኝነት ከዓለም ታላላቅ የእግር ኳስ ኮከቦች ጋር በመገናኘት ለብዙ ሰዎች ተስፋና መነሳሳትን አስተላልፏል።
በእስከዳር ይኩኑአምላክ
28 days ago
''የውቦች ንግስት''
በምህረት
#Ethiopia | ምህረት ደግፍ ትውልድና እድገቷ አዲስ አበባ ፤ በልዩ ስሙ ኮልፌ 18 ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ነው።
የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርቷን በሐምሌ 19 የመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤት ፣ ሁለተኛ ደረጃን በየካቲት 23 ት/ቤት ፣ የመሰናዶ ትምህርቷን ደግሞ በአዲስ ከተማ መሰናዶ ተከታትላ ጨርሳለች።
ቀጥሎም በኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ በመምህርነት በመመረቅ ትምህርቷን ያጠናቀቀች ሲሆን ፤ በአሁኑ ወቅትም በዚሁ ዩኒቨርሲቲ የእንግሊዘኛ ቋንቋ እና ሥነ-ጽሑፍ የመጀመሪያ ዲግሪ ተማሪ ናት።
የጋዜጠኝነት ሞያን ከከፍታ የትምህርት ሥልጠና እና የማማከር ተቋም ያጠናቀቀች ሲሆን ፤ በፋክት ቼኪንግ እና ሌሎችም ተያያዥ ሥልጠናዎችን ከሌሎች የሃገር ውስጥ እና የውጪ ተቋማት በሰርተፊኬት ማግኘት ችላለች።
ከመደበኛው ትምህርት ባሻገር ሙሉ የልጅነት ሕይወቷ ያለፈው በደብረ ገሊላ አማኑኤል እግዚአብሔር ምስሌነ ሰንበት ትምህርት ቤት ነው። አሁን ላለችበትም መሰረት የጣለችው ሰንበት ትምህርት ቤት በነበረችበት ወቅት ነው። በተለይም በሥነ-ጽሑፍ ረገድ ዝንባሌ ሊኖራት የቻለው ከልጅነት ጀምሮ በሰንበት ት/ቤት እና በመደበኛ ት/ቤት በነበራት ተሳትፎ ነው። እንደ ግጥም ፣ መነባንብ ፣ ድራማ እና ሌሎችም ላይ የበዛ ተሳትፎ ታደርግ ነበር። ይህ ተሳትፎ አሁንም ድረስ ተከትሏት በመምጣት ለፍሬ እንደደረሰ ታምናለች።
በት/ቤት ፣ በወረዳ እና በክፍለ ከተማ ብሎም በከተማ አቀፍ በነበሩ የሥነ-ጸሑፍ ውድድሮች ፣ መድረኮች እና መሰል ዝግጅቶች ላይ በመሳተፍ የተለያዩ ሽልማቶችን እና የምስጋና ወረቀቶችን ማግኘት ችላለች። በመንፈሳዊም በኩል በተመሳሳይ ሁኔታ በነበሯት ተሳትፎዎች በርካታ ሽልማቶችን አግኝታለች። እስከዛሬ ድረስም በተለያዩ የሥነ-ጸሑፍ መድረኮች ሥራዎቿን እያቀረበች ትገኛለች።
ከኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ እንደተመረቀች በአጼ ፋሲል የመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤት ለሁለት ዓመት ያህል በመምህርነት አገልግላለች። በሞያው በቆየችባቸው ጥቂት ዓመታት የተለያዩ የምስጋና እና የደረጃ ሽልማቶችን ማግኘት ችላለች።
ከዚያ በመቀጠል በተዋህዶ ሚዲያ ማዕከል ለአንድ ዓመት ያህል በፕሮግራም አዘጋጅነት የሠራች ሲሆን ፤ የራሷን መንፈሳዊ ፕሮግራሞች እና ሥራዎች በመሥራት ቆይታለች። በአሁኑ ወቅት በሐገሬ ቴሌቪዥን በከፍተኛ ሪፖርተርነት መደብ እየሠራች የምትገኝ ሲሆን ፤ ላለፈው አንድ ዓመት ያህል በዚሁ ጣቢያ የዜና ክፍል ባልደረባ በመሆን ቆይታለች።
ከልጅነት ጀምሮ የተከተላት የሥነ-ጽሑፍ ፍቅር አሁንም ድረስ ተከትሏት የመጣ ሲሆን ፤ የመጀመሪያ የሆነውንና ” የውቦች ንግሥት” ስትል የሰየመችውን መጽሐፏን ለአንባቢያን ለማድረስ ዝግጅቷን አጠናቃለች።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
በምህረት
#Ethiopia | ምህረት ደግፍ ትውልድና እድገቷ አዲስ አበባ ፤ በልዩ ስሙ ኮልፌ 18 ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ነው።
የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርቷን በሐምሌ 19 የመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤት ፣ ሁለተኛ ደረጃን በየካቲት 23 ት/ቤት ፣ የመሰናዶ ትምህርቷን ደግሞ በአዲስ ከተማ መሰናዶ ተከታትላ ጨርሳለች።
ቀጥሎም በኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ በመምህርነት በመመረቅ ትምህርቷን ያጠናቀቀች ሲሆን ፤ በአሁኑ ወቅትም በዚሁ ዩኒቨርሲቲ የእንግሊዘኛ ቋንቋ እና ሥነ-ጽሑፍ የመጀመሪያ ዲግሪ ተማሪ ናት።
የጋዜጠኝነት ሞያን ከከፍታ የትምህርት ሥልጠና እና የማማከር ተቋም ያጠናቀቀች ሲሆን ፤ በፋክት ቼኪንግ እና ሌሎችም ተያያዥ ሥልጠናዎችን ከሌሎች የሃገር ውስጥ እና የውጪ ተቋማት በሰርተፊኬት ማግኘት ችላለች።
ከመደበኛው ትምህርት ባሻገር ሙሉ የልጅነት ሕይወቷ ያለፈው በደብረ ገሊላ አማኑኤል እግዚአብሔር ምስሌነ ሰንበት ትምህርት ቤት ነው። አሁን ላለችበትም መሰረት የጣለችው ሰንበት ትምህርት ቤት በነበረችበት ወቅት ነው። በተለይም በሥነ-ጽሑፍ ረገድ ዝንባሌ ሊኖራት የቻለው ከልጅነት ጀምሮ በሰንበት ት/ቤት እና በመደበኛ ት/ቤት በነበራት ተሳትፎ ነው። እንደ ግጥም ፣ መነባንብ ፣ ድራማ እና ሌሎችም ላይ የበዛ ተሳትፎ ታደርግ ነበር። ይህ ተሳትፎ አሁንም ድረስ ተከትሏት በመምጣት ለፍሬ እንደደረሰ ታምናለች።
በት/ቤት ፣ በወረዳ እና በክፍለ ከተማ ብሎም በከተማ አቀፍ በነበሩ የሥነ-ጸሑፍ ውድድሮች ፣ መድረኮች እና መሰል ዝግጅቶች ላይ በመሳተፍ የተለያዩ ሽልማቶችን እና የምስጋና ወረቀቶችን ማግኘት ችላለች። በመንፈሳዊም በኩል በተመሳሳይ ሁኔታ በነበሯት ተሳትፎዎች በርካታ ሽልማቶችን አግኝታለች። እስከዛሬ ድረስም በተለያዩ የሥነ-ጸሑፍ መድረኮች ሥራዎቿን እያቀረበች ትገኛለች።
ከኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ እንደተመረቀች በአጼ ፋሲል የመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤት ለሁለት ዓመት ያህል በመምህርነት አገልግላለች። በሞያው በቆየችባቸው ጥቂት ዓመታት የተለያዩ የምስጋና እና የደረጃ ሽልማቶችን ማግኘት ችላለች።
ከዚያ በመቀጠል በተዋህዶ ሚዲያ ማዕከል ለአንድ ዓመት ያህል በፕሮግራም አዘጋጅነት የሠራች ሲሆን ፤ የራሷን መንፈሳዊ ፕሮግራሞች እና ሥራዎች በመሥራት ቆይታለች። በአሁኑ ወቅት በሐገሬ ቴሌቪዥን በከፍተኛ ሪፖርተርነት መደብ እየሠራች የምትገኝ ሲሆን ፤ ላለፈው አንድ ዓመት ያህል በዚሁ ጣቢያ የዜና ክፍል ባልደረባ በመሆን ቆይታለች።
ከልጅነት ጀምሮ የተከተላት የሥነ-ጽሑፍ ፍቅር አሁንም ድረስ ተከትሏት የመጣ ሲሆን ፤ የመጀመሪያ የሆነውንና ” የውቦች ንግሥት” ስትል የሰየመችውን መጽሐፏን ለአንባቢያን ለማድረስ ዝግጅቷን አጠናቃለች።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
1 month ago
u12e8u1219u12eb u1290u1343u1290u1275 u120du1245u1290u1275 u12a0u12edu12f0u1208u121d - u12e8u130bu12dcu1320u129du1290u1275u1293 u12aeu1219u1292u12acu123du1295 u1218u121du1205u122d u1218u12a9u122au12eb u1218u12abu123b (u1228/u1355) #u1208u1200u1308u122d #u1356u12f5u12abu1235u1275 #u134bu1293u1356u12f5u12abu1235u1275 #u134bu1293u121au12f2u12ebu12aeu122du1356u122cu123du1295 #fanapodcast #fanadigitalmedia #fanamediacorporation #poodkaastiifaanaa #fanadigitalmedia #u0641u0627 ","delight_ranges":[],"image_ranges":[],"inline_style_ranges":[],"aggregated_ranges":[],"ranges":[{"entity":{"__typename":"Hashtag","__isEntity":"Hashtag","url":"https://www.facebook.com/h...
የሙያ ነፃነት ልቅነት አይደለም - የጋዜጠኝነትና ኮሙኒኬሽን መምህር መኩሪያ መካሻ (ረ/ፕ) #ለሀገር #ፖድካስት #ፋናፖድካስት #ፋናሚዲያኮርፖሬሽን #fanapodcast #fanadigitalmedia #fanamediacorporation #poodkaastiifaanaa #fanadigitalmedia #فا
1 month ago
የሙያ ነፃነት ልቅነት አይደለም -የጋዜጠኝነትና ኮሙኒኬሽን መምህር መኩሪያ መካሻ (ረ/ፕ)
ዛሬ ከቀኑ 8:00 በፋና ፖድካስት ይጠብቁን
#ለሀገር #ፖድካስት #ፋናፖድካስት #ፋናሚዲያኮርፖሬሽን #fanapodcast #fanadigitalmedia #fanamediacorporation #poodkaastiifaanaa #fanadigitalmedia #فا
1 month ago
ያልተመዘገቡ ዲጂታል ሚዲያዎችን ወደ ሕጋዊ መስመር የሚያመጣ የአዋጅ ማሻሻያ ሊደረግ ነው
#ethiopia | የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን አሁን ላይ በበይነ መረብ (ዲጂታል) ሚዲያው ዘርፍ የሚታየውን የሐሰተኛ መረጃና የጥላቻ ንግግር ስርጭት ለመግታት፣ ያልተመዘገቡ ሚዲያዎችን ወደ ሕጋዊ የምዝገባ ሥርዓት የሚያስገባ የአዋጅ ማሻሻያ ሊያደርግ መሆኑን አስታወቀ።
የባለሥልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ ኃይማኖት ዘለቀ ይህንን የገለጹት፣ “ብቃት ያለው የበይነ መረብ መገናኛ ብዙኃን ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም” በሚል መሪ ቃል በተዘጋጀ የሚዲያ ኮንፈረንስ ላይ ባደረጉት ንግግር ነው።
ዳይሬክተሯ በዚሁ ጊዜ እንዳብራሩት፣ ከአመታት በኋላ በሚዲያው ዘርፍ የተደረገውን ሰፊ ሪፎርም ተከትሎ ድረ-ገጾችን የማፈንና የመዝጋት አሰራር በመቅረቱ በኢትዮጵያ ውስጥ በርካታ ጠንካራና ሚዛናዊ የዲጂታል ሚዲያዎች ሊፈጠሩ ችለዋል።
ይሁን እንጂ ይህንን ምቹ ሁኔታ ተጠቅመው የሕዝብን አመኔታ ካገኙት ባሻገር፣ የተወሰኑት የዲጅታል ሚዲያዎች የሐሰተኛ መረጃና የጥላቻ ንግግር የሚያሰራጩ እንዲሁም የሀገርን ሉዓላዊነትና የጋራ ደህንነት አደጋ ላይ የሚጥሉ አካላት መበራከታቸውን ዳይሬክተሯ በንግግራቸው አብራርተዋል።
ይህንን አሳሳቢ ተግዳሮት ለመቅረፍም ባለሥልጣኑ በርካታ ተከታዮች እያሏቸው ነገር ግን ሳይመዘገቡ በዘፈቀደ የሚንቀሳቀሱ ሚዲያዎችን ሕጋዊ ለማድረግ የሚያስችል የአዋጅ ማሻሻያ ዝግጅት እያጠናቀቀ መሆኑን አስታውቀዋል።
አዲሱ አሰራር በፓርላማ ጸድቆ ሲተገበርም፣ ማንኛውም ዲጂታል ሚዲያ በሕጋዊ ማዕቀፍ ውስጥ ገብቶ ለሀገር ሰላምና ለብሔራዊ ጥቅም በኃላፊነት ስሜት መሥራት እንደሚኖርበት አሳስበዋል።
የባለሥልጣኑ ዋና ዓላማ ተቋማትን መቅጣት፣ መዝጋት ወይም መቆጣጠር ብቻ አለመሆኑን ያነሱት ወ/ሮ ኃይማኖት፣ ተቋሙ ከቁጥጥር ይልቅ በአቅም ግንባታ፣ በምክክር እና ልዩ ልዩ ድጋፎችን በማድረግ ላይ እንደሚያተኩር ገልጸዋል።
በመሆኑም ሕጋዊ ሆነው ለሚመዘገቡ የዲጂታል ሚዲያ ባለሙያዎች የጋዜጠኝነት መታወቂያ ከመስጠት ጀምሮ የፋይናንስና የቴክኒክ ድጋፎችን የሚያካትቱ የማበረታቻ ሥርዓቶች እንደሚዘረጉ ተናግረዋል።
በመጨረሻም የዘርፉ ባለሙያዎች እርስ በርስ የሚተራረሙበት፣ ለሙያዊ ሥነ-ምግባር መከበር የሚቆምና በሌሎች ሀገራት እንደሚታየው ራሳቸውን በራሳቸው እንዲቆጣጠሩ የሚያስችል ጠንካራ የጋዜጠኞች ማኅበር በማቋቋም በጋራ እንዲሰሩ ጥሪያቸውን አቅርበዋል።
በጌትነት ተመስገን
📷 ኢመብባ
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
#ethiopia #ethiopianmedia #digitalmedia #journalism #mediaregulation #ethiopianews
#ethiopia | የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን አሁን ላይ በበይነ መረብ (ዲጂታል) ሚዲያው ዘርፍ የሚታየውን የሐሰተኛ መረጃና የጥላቻ ንግግር ስርጭት ለመግታት፣ ያልተመዘገቡ ሚዲያዎችን ወደ ሕጋዊ የምዝገባ ሥርዓት የሚያስገባ የአዋጅ ማሻሻያ ሊያደርግ መሆኑን አስታወቀ።
የባለሥልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ ኃይማኖት ዘለቀ ይህንን የገለጹት፣ “ብቃት ያለው የበይነ መረብ መገናኛ ብዙኃን ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም” በሚል መሪ ቃል በተዘጋጀ የሚዲያ ኮንፈረንስ ላይ ባደረጉት ንግግር ነው።
ዳይሬክተሯ በዚሁ ጊዜ እንዳብራሩት፣ ከአመታት በኋላ በሚዲያው ዘርፍ የተደረገውን ሰፊ ሪፎርም ተከትሎ ድረ-ገጾችን የማፈንና የመዝጋት አሰራር በመቅረቱ በኢትዮጵያ ውስጥ በርካታ ጠንካራና ሚዛናዊ የዲጂታል ሚዲያዎች ሊፈጠሩ ችለዋል።
ይሁን እንጂ ይህንን ምቹ ሁኔታ ተጠቅመው የሕዝብን አመኔታ ካገኙት ባሻገር፣ የተወሰኑት የዲጅታል ሚዲያዎች የሐሰተኛ መረጃና የጥላቻ ንግግር የሚያሰራጩ እንዲሁም የሀገርን ሉዓላዊነትና የጋራ ደህንነት አደጋ ላይ የሚጥሉ አካላት መበራከታቸውን ዳይሬክተሯ በንግግራቸው አብራርተዋል።
ይህንን አሳሳቢ ተግዳሮት ለመቅረፍም ባለሥልጣኑ በርካታ ተከታዮች እያሏቸው ነገር ግን ሳይመዘገቡ በዘፈቀደ የሚንቀሳቀሱ ሚዲያዎችን ሕጋዊ ለማድረግ የሚያስችል የአዋጅ ማሻሻያ ዝግጅት እያጠናቀቀ መሆኑን አስታውቀዋል።
አዲሱ አሰራር በፓርላማ ጸድቆ ሲተገበርም፣ ማንኛውም ዲጂታል ሚዲያ በሕጋዊ ማዕቀፍ ውስጥ ገብቶ ለሀገር ሰላምና ለብሔራዊ ጥቅም በኃላፊነት ስሜት መሥራት እንደሚኖርበት አሳስበዋል።
የባለሥልጣኑ ዋና ዓላማ ተቋማትን መቅጣት፣ መዝጋት ወይም መቆጣጠር ብቻ አለመሆኑን ያነሱት ወ/ሮ ኃይማኖት፣ ተቋሙ ከቁጥጥር ይልቅ በአቅም ግንባታ፣ በምክክር እና ልዩ ልዩ ድጋፎችን በማድረግ ላይ እንደሚያተኩር ገልጸዋል።
በመሆኑም ሕጋዊ ሆነው ለሚመዘገቡ የዲጂታል ሚዲያ ባለሙያዎች የጋዜጠኝነት መታወቂያ ከመስጠት ጀምሮ የፋይናንስና የቴክኒክ ድጋፎችን የሚያካትቱ የማበረታቻ ሥርዓቶች እንደሚዘረጉ ተናግረዋል።
በመጨረሻም የዘርፉ ባለሙያዎች እርስ በርስ የሚተራረሙበት፣ ለሙያዊ ሥነ-ምግባር መከበር የሚቆምና በሌሎች ሀገራት እንደሚታየው ራሳቸውን በራሳቸው እንዲቆጣጠሩ የሚያስችል ጠንካራ የጋዜጠኞች ማኅበር በማቋቋም በጋራ እንዲሰሩ ጥሪያቸውን አቅርበዋል።
በጌትነት ተመስገን
📷 ኢመብባ
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
#ethiopia #ethiopianmedia #digitalmedia #journalism #mediaregulation #ethiopianews
1 month ago
የቱሪዝም መዳረሻዎችን በዘመናዊ ስልት ለማስተዋወቅ የሚዲያ ፎረም ተመሰረተ
#ethiopia | የሀገሪቱን የቱሪዝም መዳረሻዎች በዘመናዊ መንገድ ለዓለም ለማስተዋወቅና የመረጃ ልውውጡን በተቀናጀ ስልት ለመምራት የሚያስችል የቱሪዝም ኮሙኒኬሽን ስልጠና በአዳማ ከተማ የተካሄደ ሲሆን፣ በዚሁ መድረክ ላይ የቱሪዝም ሚዲያ ፎረም በይፋ ተመስርቷል።
የፌደራልና የክልል የቱሪዝም ቢሮ የሕዝብ ግንኙነት ባለሙያዎችን እንዲሁም የተለያዩ የሚዲያ ተቋማት ጋዜጠኞችንና ኃላፊዎችን ያሳተፈው ይህ መርሃ-ግብር፣ በዘርፉ የሚታየውን የተበታተነ የኮሙኒኬሽን ስራ በማስቀረት የተቀናጀ የቱሪዝም ዲፕሎማሲ ለመገንባት ያለመ ነው።
በመድረኩ ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የቱሪዝም ሚኒስቴር ሚኒስትር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ንጉሴ ክብሩ፣ መንግስት ለዘርፉ ልዩ ትኩረት በመስጠት ከሀገሪቱ አምስት ዋና ዋና የኢኮኖሚ አመንጭ ዘርፎች ውስጥ አንዱ አድርጎ እየሰራበት መሆኑን ገልጸዋል።
በርካታ አዳዲስ መዳረሻዎችን የማልማትና በነባሮቹ ላይ እሴት የመጨመር ስራዎች በስፋት እየተከናወኑ መሆኑን የጠቀሱት ኃላፊው፣ እነዚህን ጸጋዎች በዘመናዊ ስልት ለአለም ማስተዋወቅና የሀገርን በጎ ገጽታ መገንባት የሚዲያና የኮሙኒኬሽን ባለሙያዎች ሊወጡት የሚገባ ዋነኛ ሀገራዊ ኃላፊነት መሆኑን አጽንኦት ሰጥተዋል።
ለተሳታፊዎቹ ስልጠና የሰጡት የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጋዜጠኝነትና ኮሙኒኬሽን ትምህርት ቤት መምህር ጌታቸው ድንቁ (ዶ/ር) በበኩላቸው፣ የቱሪዝም ሚዲያ ስራ ከተለመደው የዜና አሰራር ወጥቶ ሳቢ፣ ታሪክን መሰረት ያደረገ እና ዲጂታል አማራጮችን የተጠቀመ ሊሆን እንደሚገባ አብራርተዋል።
አዲስ የተመሰረተው የሚዲያ ፎረም እስካሁን በዘርፉ በዘልማድ ከሚታየውና ለአንድ ወቅት ብቻ ከሚደረግ የመረጃ ልውውጥ ባለፈ፣ በክልሎችና በሚዲያ ተቋማት መካከል ወጥነት ያለውና ቀጣይነት ያለው የመረጃ ቅብብሎሽ ስርዓት በመዘርጋት ለቱሪዝም እድገት ትልቅ አቅም እንደሚፈጥር ታምኖበታል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
#ethiopia | የሀገሪቱን የቱሪዝም መዳረሻዎች በዘመናዊ መንገድ ለዓለም ለማስተዋወቅና የመረጃ ልውውጡን በተቀናጀ ስልት ለመምራት የሚያስችል የቱሪዝም ኮሙኒኬሽን ስልጠና በአዳማ ከተማ የተካሄደ ሲሆን፣ በዚሁ መድረክ ላይ የቱሪዝም ሚዲያ ፎረም በይፋ ተመስርቷል።
የፌደራልና የክልል የቱሪዝም ቢሮ የሕዝብ ግንኙነት ባለሙያዎችን እንዲሁም የተለያዩ የሚዲያ ተቋማት ጋዜጠኞችንና ኃላፊዎችን ያሳተፈው ይህ መርሃ-ግብር፣ በዘርፉ የሚታየውን የተበታተነ የኮሙኒኬሽን ስራ በማስቀረት የተቀናጀ የቱሪዝም ዲፕሎማሲ ለመገንባት ያለመ ነው።
በመድረኩ ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የቱሪዝም ሚኒስቴር ሚኒስትር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ንጉሴ ክብሩ፣ መንግስት ለዘርፉ ልዩ ትኩረት በመስጠት ከሀገሪቱ አምስት ዋና ዋና የኢኮኖሚ አመንጭ ዘርፎች ውስጥ አንዱ አድርጎ እየሰራበት መሆኑን ገልጸዋል።
በርካታ አዳዲስ መዳረሻዎችን የማልማትና በነባሮቹ ላይ እሴት የመጨመር ስራዎች በስፋት እየተከናወኑ መሆኑን የጠቀሱት ኃላፊው፣ እነዚህን ጸጋዎች በዘመናዊ ስልት ለአለም ማስተዋወቅና የሀገርን በጎ ገጽታ መገንባት የሚዲያና የኮሙኒኬሽን ባለሙያዎች ሊወጡት የሚገባ ዋነኛ ሀገራዊ ኃላፊነት መሆኑን አጽንኦት ሰጥተዋል።
ለተሳታፊዎቹ ስልጠና የሰጡት የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጋዜጠኝነትና ኮሙኒኬሽን ትምህርት ቤት መምህር ጌታቸው ድንቁ (ዶ/ር) በበኩላቸው፣ የቱሪዝም ሚዲያ ስራ ከተለመደው የዜና አሰራር ወጥቶ ሳቢ፣ ታሪክን መሰረት ያደረገ እና ዲጂታል አማራጮችን የተጠቀመ ሊሆን እንደሚገባ አብራርተዋል።
አዲስ የተመሰረተው የሚዲያ ፎረም እስካሁን በዘርፉ በዘልማድ ከሚታየውና ለአንድ ወቅት ብቻ ከሚደረግ የመረጃ ልውውጥ ባለፈ፣ በክልሎችና በሚዲያ ተቋማት መካከል ወጥነት ያለውና ቀጣይነት ያለው የመረጃ ቅብብሎሽ ስርዓት በመዘርጋት ለቱሪዝም እድገት ትልቅ አቅም እንደሚፈጥር ታምኖበታል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
Sponsored by
Surafel
1 month ago
የአንድ ጀግና አባት ህልፈት የትናንት ጉልበት የዛሬው የቤተሰብ ጣጣ
👉ሼር በማድረግ ተባበሩ
ባሳለፍነው ሳምንት ሰኔ 19 ቀን 2018 ዓ.ም. የተሰማው መራር ዜና፣ የብዙዎችን ልብ ሰብሮ አልፏል።
የፌደራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን የሚዲያ ኃላፊ እና የአዲስ ሚዲያ ኔትወርክ (አዲስ ቴሌቪዥን) ጋዜጠኛ የነበረው ሳህለገብርኤል፤ ለሀገሩ፣ ለሙያው እና ለቤተሰቡ የነበረው ቁርጠኝነት አርአያ የሚባል ነበር።
ለ20 ዓመታት በፌደራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን ውስጥ ፍትህን ለማስፈንና የህግ ታራሚዎችን ለመቅረጽ የነበረው ጉልበትና እውቀት፤ ከሙያው ባለፈ ለሀገር የነበረው ፍቅር መገለጫ ነበር።
በተለይም ከ2008 ዓ.ም. ጀምሮ በአዲስ ሚዲያ ኔትወርክ ያሳየው ትጋት፣ በጋዜጠኝነት ሙያው ውስጥ ለተተኪዎች ትልቅ ትምህርት ነው።
ከሞቱ ሁለት ቀናት በፊት እንኳ ለተቋሙ ማሻሻያ ትልቅ እቅድ አውጥቶ የነበረው ሳህለገብርኤል፣ ዛሬ በሞት ተነጥቆ የሶስት የዋህ ልጆች አባትና ባለቤቱን በከፍተኛ ሁኔታ ጥሎ አልፏል።
የዛሬው አሳዛኝ እውነታ ግን የሞቱ ዜና ብቻ ሳይሆን፣ ከኋላው የቀሩት ቤተሰቦቹ በከፍተኛ የኑሮ ችግር ውስጥ መውደቃቸው ነው።
ጋዜጠኛ ሳህለገብርኤል በህይወት በነበረበት ወቅት ለሌሎች የነበረው ደግነት፣ ዛሬ ለቤተሰቡ መመለስ አለበት። በፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን የአባሎች መኖሪያ ካምፕ የሚኖሩት ቤተሰቦቹ፣ የወደፊታቸው እጅግ አሳሳቢ ሆኗል።
ለልጆቹ መኖሪያ፡ መጠለያ ማግኘት አቅማቸው በላይ ሆኗል።
የልጆቹ የወደፊት ተስፋ የሆነው ትምህርት እንዲቀጥል ድጋፍ ይፈልጋሉ።
በበዓላት እና በዕለት ተዕለት ኑሮአቸው ከጎናቸው የሚቆም ሰው ይሻሉ።
ይህ ጥሪ ለክቡርት ከንቲባ አዳነች አበቤ፣ ለፌደራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን ኮሚሽነር ጄኔራል የኑስ ሙሉ፣ ለበጎ አድራጊ ድርጅቶች እና ለሰብአዊነት ለሚቆሙ ወገኖች ሁሉ የሚቀርብ የአደራ ጥሪ ነው።
አጋርነታችሁን ግለጹ
የሳህለገብርኤልን አሻራ ለማስታወስ እና ቤተሰቡን ከመከራ ለመታደግ፣ ያላችሁን ትንሽ ድጋፍ እንድትለግሱ በአክብሮት እንጠይቃለን።
ባንክ: ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ (CBE)
የሂሳብ ቁጥር: 1000081155457
ሙሉ ስም: ጎጃም ይበልጣል ከበደ
ለቤተሰቦቹ የምናደርገው እያንዳንዱ እርዳታ፣ የጀግናውን ጋዜጠኛ ነፍስ የሚያሳርፍ፣ ለልጆቹ ደግሞ ተስፋን የሚሰጥ ነው።
#ሼርርርርርር
👉ሼር በማድረግ ተባበሩ
ባሳለፍነው ሳምንት ሰኔ 19 ቀን 2018 ዓ.ም. የተሰማው መራር ዜና፣ የብዙዎችን ልብ ሰብሮ አልፏል።
የፌደራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን የሚዲያ ኃላፊ እና የአዲስ ሚዲያ ኔትወርክ (አዲስ ቴሌቪዥን) ጋዜጠኛ የነበረው ሳህለገብርኤል፤ ለሀገሩ፣ ለሙያው እና ለቤተሰቡ የነበረው ቁርጠኝነት አርአያ የሚባል ነበር።
ለ20 ዓመታት በፌደራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን ውስጥ ፍትህን ለማስፈንና የህግ ታራሚዎችን ለመቅረጽ የነበረው ጉልበትና እውቀት፤ ከሙያው ባለፈ ለሀገር የነበረው ፍቅር መገለጫ ነበር።
በተለይም ከ2008 ዓ.ም. ጀምሮ በአዲስ ሚዲያ ኔትወርክ ያሳየው ትጋት፣ በጋዜጠኝነት ሙያው ውስጥ ለተተኪዎች ትልቅ ትምህርት ነው።
ከሞቱ ሁለት ቀናት በፊት እንኳ ለተቋሙ ማሻሻያ ትልቅ እቅድ አውጥቶ የነበረው ሳህለገብርኤል፣ ዛሬ በሞት ተነጥቆ የሶስት የዋህ ልጆች አባትና ባለቤቱን በከፍተኛ ሁኔታ ጥሎ አልፏል።
የዛሬው አሳዛኝ እውነታ ግን የሞቱ ዜና ብቻ ሳይሆን፣ ከኋላው የቀሩት ቤተሰቦቹ በከፍተኛ የኑሮ ችግር ውስጥ መውደቃቸው ነው።
ጋዜጠኛ ሳህለገብርኤል በህይወት በነበረበት ወቅት ለሌሎች የነበረው ደግነት፣ ዛሬ ለቤተሰቡ መመለስ አለበት። በፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን የአባሎች መኖሪያ ካምፕ የሚኖሩት ቤተሰቦቹ፣ የወደፊታቸው እጅግ አሳሳቢ ሆኗል።
ለልጆቹ መኖሪያ፡ መጠለያ ማግኘት አቅማቸው በላይ ሆኗል።
የልጆቹ የወደፊት ተስፋ የሆነው ትምህርት እንዲቀጥል ድጋፍ ይፈልጋሉ።
በበዓላት እና በዕለት ተዕለት ኑሮአቸው ከጎናቸው የሚቆም ሰው ይሻሉ።
ይህ ጥሪ ለክቡርት ከንቲባ አዳነች አበቤ፣ ለፌደራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን ኮሚሽነር ጄኔራል የኑስ ሙሉ፣ ለበጎ አድራጊ ድርጅቶች እና ለሰብአዊነት ለሚቆሙ ወገኖች ሁሉ የሚቀርብ የአደራ ጥሪ ነው።
አጋርነታችሁን ግለጹ
የሳህለገብርኤልን አሻራ ለማስታወስ እና ቤተሰቡን ከመከራ ለመታደግ፣ ያላችሁን ትንሽ ድጋፍ እንድትለግሱ በአክብሮት እንጠይቃለን።
ባንክ: ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ (CBE)
የሂሳብ ቁጥር: 1000081155457
ሙሉ ስም: ጎጃም ይበልጣል ከበደ
ለቤተሰቦቹ የምናደርገው እያንዳንዱ እርዳታ፣ የጀግናውን ጋዜጠኛ ነፍስ የሚያሳርፍ፣ ለልጆቹ ደግሞ ተስፋን የሚሰጥ ነው።
#ሼርርርርርር
1 month ago
ማኑዋል መኪና መንዳት የአንጎልን የመሥራት ብቃት እንደሚያሳድግ አዲስ ጥናት አመለከተ
የማኑዋል መኪና አነዳድ ከተለመደው የመንዳት ልምድ ባለፈ ለአእምሮ ጤና ከፍተኛ ጠቀሜታ እንዳለው በጃፓን የተደረገ አዲስ ጥናት ጠቆመ። ጥናቱ እንደሚያመለክተው ማኑዋል መኪናዎችን ማዘወር ለአውቶማቲክ መኪናዎች ከሚሰጠው ትኩረት ይልቅ ለአንጎል የማስታወስ፣ ትኩረትን የመሰብሰብ እና ውሳኔ የመስጠት ብቃትን በከፍተኛ ሁኔታ ያነቃቃል።
ይህ ግኝት ይፋ የሆነው በጃፓኑ “ቤስት ካር ዌብ” (Best Car Web) የጋዜጠኝነት መድረክ ሲሆን፣ ጥናቱን ያካሄዱት ደግሞ በቶሆኩ ዩኒቨርሲቲ የልማት፣ እርጅና እና ካንሰር ምርምር ተቋም ፕሮፌሰር የሆኑት ርዩታ ካዋሺማ ናቸው። ፕሮፌሰሩ ቀደም ሲል በዓለም አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ ተወዳጅነትን ያተረፈውን የኒንቴንዶ “ብሬይን ኤጅ” የአእምሮ ማሳያ ጨዋታዎች በስተጀርባ ያለውን የሳይንስ መሠረት ያዘጋጁ ታዋቂ የነርቭ ሳይንቲስት ናቸው። በሳቸው ምርምር መሠረት ማኑዋል መኪና በሚነዳበት ወቅት የሚፈለጉት ተከታታይ ተግባራት ከፍተኛ የእውቀት ተግባራትን የሚያከናውነውን የአንጎል የፊት ክፍል ያነቃቁታል።
የማኑዋል መኪና አሽከርካሪዎች ክላች መርገጥን፣ ማርሽ መቀየርን፣ የነዳጅ መቆጣጠሪያን (throttle) ማስተካከልን እና በተመሳሳይ ሰዓት የትራፊክ ፍሰቱን መከታተልን በአንድ ላይ ማቀናጀት ይጠበቅባቸዋል። ተመራማሪዎቹ እንዳረጋገጡት ይህ በአንድ ጊዜ በርካታ ሥራዎችን የመሥራት ሂደት አእምሮ ያለማቋረጥ ንቁ ሆኖ መረጃዎችን እንዲያሰላስል የሚያስገድደው በመሆኑ፣ ለአንጎል የፊት ክፍል ታላቅ የዕለት ተዕለት የስፖርት እንቅስቃሴ ሆኖ ያገለግላል።
Seledadotio
Seledadotio
የማኑዋል መኪና አነዳድ ከተለመደው የመንዳት ልምድ ባለፈ ለአእምሮ ጤና ከፍተኛ ጠቀሜታ እንዳለው በጃፓን የተደረገ አዲስ ጥናት ጠቆመ። ጥናቱ እንደሚያመለክተው ማኑዋል መኪናዎችን ማዘወር ለአውቶማቲክ መኪናዎች ከሚሰጠው ትኩረት ይልቅ ለአንጎል የማስታወስ፣ ትኩረትን የመሰብሰብ እና ውሳኔ የመስጠት ብቃትን በከፍተኛ ሁኔታ ያነቃቃል።
ይህ ግኝት ይፋ የሆነው በጃፓኑ “ቤስት ካር ዌብ” (Best Car Web) የጋዜጠኝነት መድረክ ሲሆን፣ ጥናቱን ያካሄዱት ደግሞ በቶሆኩ ዩኒቨርሲቲ የልማት፣ እርጅና እና ካንሰር ምርምር ተቋም ፕሮፌሰር የሆኑት ርዩታ ካዋሺማ ናቸው። ፕሮፌሰሩ ቀደም ሲል በዓለም አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ ተወዳጅነትን ያተረፈውን የኒንቴንዶ “ብሬይን ኤጅ” የአእምሮ ማሳያ ጨዋታዎች በስተጀርባ ያለውን የሳይንስ መሠረት ያዘጋጁ ታዋቂ የነርቭ ሳይንቲስት ናቸው። በሳቸው ምርምር መሠረት ማኑዋል መኪና በሚነዳበት ወቅት የሚፈለጉት ተከታታይ ተግባራት ከፍተኛ የእውቀት ተግባራትን የሚያከናውነውን የአንጎል የፊት ክፍል ያነቃቁታል።
የማኑዋል መኪና አሽከርካሪዎች ክላች መርገጥን፣ ማርሽ መቀየርን፣ የነዳጅ መቆጣጠሪያን (throttle) ማስተካከልን እና በተመሳሳይ ሰዓት የትራፊክ ፍሰቱን መከታተልን በአንድ ላይ ማቀናጀት ይጠበቅባቸዋል። ተመራማሪዎቹ እንዳረጋገጡት ይህ በአንድ ጊዜ በርካታ ሥራዎችን የመሥራት ሂደት አእምሮ ያለማቋረጥ ንቁ ሆኖ መረጃዎችን እንዲያሰላስል የሚያስገድደው በመሆኑ፣ ለአንጎል የፊት ክፍል ታላቅ የዕለት ተዕለት የስፖርት እንቅስቃሴ ሆኖ ያገለግላል።
Seledadotio
Seledadotio
1 month ago
ከሀዘን በዘለለ ምን እናድርግ ?
#ethiopia | ጋዜጠኛ ም/ኢንስፔክተር ሳህለገብርኤል ይትባረክ የፌደራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን የሚዲያ ሃላፊ እንዲሁም የአዲስ ሚዲያ ኔትወርክ ዜና አንባቢ በመሆን ሰኔ 19 ቀን 2018 ዓ.ም. በድንገት ህይወቱ እስካለፈበት ቀን ድረስ ለሀገሩ ብሎም ለተቋሙ የወደፊት መልካም ገፅታ እውቀቱን ጉልበቱን ሳይሰስት ሲያገለግል ቆይቷል።
ጋዜጠኛ ም/ኢንስፔክተር ሳህለገብርኤል ይትባረክ በ18 ዓመቱ የፌደራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽንን በመቀላቀል ለ20 አመታት ያህል ፍትህን መሠረት በማድረግ የህግ ታራሚዎችን በማረምና ማነፅ ሥራዎች ላይ ጉልህ አሻራውን ያሳረፈ ለዛም ማሳያ ከማለፉ ከሁለት ቀን በፊት ለተቋሙን ካለበት ደረጃ ለማሻሻል ያለውን የወደፊት ዓላማውን ከማስቀመጡም በተጨማሪም ያለውን ትርፍ ጊዜ በመጠቀም ከ2008 ዓ/ም ጀምሮ በአዲስ ቴሌቭዥን(አዲስ ሚዲያ ኔትወርክ) ለ10 አመታት ያህል በጋዜጠኝነት ሙያው ለሀገሩ በትጋት አገልግሏል::
ጋዜጠኛ ም/ኢ/ር ሳህለገበርኤል ይትባረክ እስከ ህይወቱ ህልፈት ድረስ ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይል ሙሉ ጊዜውን ለሁለቱ ተቋማት በተከበረ ሙያው አገልግሏል።
በመሆኑም ለዚህ መራር እና አስደንጋጭ የሣህለገብርኤል ድንገተኛ ሞት በቀጥታ ተጎጅ ለሆኑት 3 ልጆቹ እና ባለቤቱ ከጎናቸው በመሆን ድጋፍ እንዲደረግላቸው እና በማህበረሰቡ ውስጥ የፈጠረውን አሳዛኝ ክስተት ከተጎጅወች ቤተሰብ ጎን በመቆም በዚህ ሁለገብ እንቁ ጋዜጠኛ ምክትል ኢንስፔክተር የተሰማንን ጥልቅ ሀዘንን በቀጥታ የፌደራል ማረሚያ ቤት ሀላፊ ክብር ኮሚሽነር ጄኔራል የኑስ ሙሉ እና የአዲስ ሚዲያ ኔትወርክ የስራ ባልደረቦች እና ክቡርት ከንቲባ አዳነች አበቤ በሀዘን የተጎዳውን ህዝብ እና ቤተሰቦችን በሚታይ ተግባር አፅናንቶ አርዓያ የሚሆን በጎ ስራ እንዲሰራ እየጠየቅን ይህንን አይከን የሆነ ወጣት ሁሉም ሰው በይቻላል መንፈስ እንዲያስታውሰው እንጠይቃለን ቤተሰቦቹ ለመንግስት ተቋማት፣ ለግብረ ሰናይ ድርጅቶች እና ለበጎ አድራጊ ግለሰቦችን ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።
በፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን የአባሎች መኖሪያ ካምፕ የሚኖሩት የጋዜጠኛ ም/ኢንስፔክተር ሳህለገብርኤል ይትባረክ ቤተሰቦች ለከፍተኛ ችግር ከመዳረጋቸው በፊት ለልጆቹ ምቹ የመኖሪያ ቤት እንዲያገኙ ከማድረግ በተጨማሪ ትምህርታቸውን ባሉበት ሁኔታ ለማስቀጠል እንዲሁም በበዓላት ወቅት ከልጆቹ ጎን መሆን እንደሚገባ ለሚመለከታቸው ተቋማትና አካላት መልዕክቱን ያስተላልፋል።
1000081155457
ጎጃም ይበልጣል ከበደ
ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
#ethiopia | ጋዜጠኛ ም/ኢንስፔክተር ሳህለገብርኤል ይትባረክ የፌደራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን የሚዲያ ሃላፊ እንዲሁም የአዲስ ሚዲያ ኔትወርክ ዜና አንባቢ በመሆን ሰኔ 19 ቀን 2018 ዓ.ም. በድንገት ህይወቱ እስካለፈበት ቀን ድረስ ለሀገሩ ብሎም ለተቋሙ የወደፊት መልካም ገፅታ እውቀቱን ጉልበቱን ሳይሰስት ሲያገለግል ቆይቷል።
ጋዜጠኛ ም/ኢንስፔክተር ሳህለገብርኤል ይትባረክ በ18 ዓመቱ የፌደራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽንን በመቀላቀል ለ20 አመታት ያህል ፍትህን መሠረት በማድረግ የህግ ታራሚዎችን በማረምና ማነፅ ሥራዎች ላይ ጉልህ አሻራውን ያሳረፈ ለዛም ማሳያ ከማለፉ ከሁለት ቀን በፊት ለተቋሙን ካለበት ደረጃ ለማሻሻል ያለውን የወደፊት ዓላማውን ከማስቀመጡም በተጨማሪም ያለውን ትርፍ ጊዜ በመጠቀም ከ2008 ዓ/ም ጀምሮ በአዲስ ቴሌቭዥን(አዲስ ሚዲያ ኔትወርክ) ለ10 አመታት ያህል በጋዜጠኝነት ሙያው ለሀገሩ በትጋት አገልግሏል::
ጋዜጠኛ ም/ኢ/ር ሳህለገበርኤል ይትባረክ እስከ ህይወቱ ህልፈት ድረስ ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይል ሙሉ ጊዜውን ለሁለቱ ተቋማት በተከበረ ሙያው አገልግሏል።
በመሆኑም ለዚህ መራር እና አስደንጋጭ የሣህለገብርኤል ድንገተኛ ሞት በቀጥታ ተጎጅ ለሆኑት 3 ልጆቹ እና ባለቤቱ ከጎናቸው በመሆን ድጋፍ እንዲደረግላቸው እና በማህበረሰቡ ውስጥ የፈጠረውን አሳዛኝ ክስተት ከተጎጅወች ቤተሰብ ጎን በመቆም በዚህ ሁለገብ እንቁ ጋዜጠኛ ምክትል ኢንስፔክተር የተሰማንን ጥልቅ ሀዘንን በቀጥታ የፌደራል ማረሚያ ቤት ሀላፊ ክብር ኮሚሽነር ጄኔራል የኑስ ሙሉ እና የአዲስ ሚዲያ ኔትወርክ የስራ ባልደረቦች እና ክቡርት ከንቲባ አዳነች አበቤ በሀዘን የተጎዳውን ህዝብ እና ቤተሰቦችን በሚታይ ተግባር አፅናንቶ አርዓያ የሚሆን በጎ ስራ እንዲሰራ እየጠየቅን ይህንን አይከን የሆነ ወጣት ሁሉም ሰው በይቻላል መንፈስ እንዲያስታውሰው እንጠይቃለን ቤተሰቦቹ ለመንግስት ተቋማት፣ ለግብረ ሰናይ ድርጅቶች እና ለበጎ አድራጊ ግለሰቦችን ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።
በፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን የአባሎች መኖሪያ ካምፕ የሚኖሩት የጋዜጠኛ ም/ኢንስፔክተር ሳህለገብርኤል ይትባረክ ቤተሰቦች ለከፍተኛ ችግር ከመዳረጋቸው በፊት ለልጆቹ ምቹ የመኖሪያ ቤት እንዲያገኙ ከማድረግ በተጨማሪ ትምህርታቸውን ባሉበት ሁኔታ ለማስቀጠል እንዲሁም በበዓላት ወቅት ከልጆቹ ጎን መሆን እንደሚገባ ለሚመለከታቸው ተቋማትና አካላት መልዕክቱን ያስተላልፋል።
1000081155457
ጎጃም ይበልጣል ከበደ
ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
1 month ago
የጋዜጠኛ ሳህለገብርኤል ይትባረክ አስከሬን በፌደራል ማረሚያ ቤት ሽኝት ተደረገለት
#ethiopia | ሳህለገብርኤል ይትባረክ አስከሬን ቤተሰቦቹ፣ ወዳጅ ዘመዶቹና የሥራ ባልደረቦቹ በተገኙበት በFederal Prison Commission የሽኝት ሥነ ሥርዓት ተካሂዶለታል።
በሥነ ሥርዓቱ ላይ የAddis Media Network እና የፌደራል ማረሚያ ቤት አመራሮች የአበባ ጉንጉን በማኖር ክብራቸውን ገልጸዋል።
ሳህለገብርኤል በጎጃም ቢቸና ተወልዶ ያደገ ሲሆን፣ በ18 ዓመቱ የፌደራል ማረሚያ ፖሊስን በመቀላቀል ከፖሊስ አባልነት እስከ ምክትል ኢንስፔክተርነት በታማኝነት አገልግሏል።
ከሙያው ጎን ለጎን የልጅነት ህልሙ የነበረውን የጋዜጠኝነት ሙያ በBahir Dar University በመማር የመጀመሪያ ዲግሪውን አግኝቶ በሙያው በትጋት ሲያገለግል ቆይቷል።
የሙያ ባልደረቦቹና አመራሮቹ ሳህለገብርኤል በትሕትናው፣ በሥራ ወዳድነቱ፣ በታማኝነቱና በመልካም ሥነ ምግባሩ የሚታወቅ እና ለብዙዎች አርአያ የነበረ ጋዜጠኛ እንደነበር አስታውሰዋል።
ሳህለገብርኤል ሰኔ 19 ቀን 2018 ዓ.ም. በድንገት ህይወቱ ያለፈ ሲሆን፣ ባለትዳርና የሦስት ልጆች አባት ነበር።
ሥርዓተ ቀብሩም በትውልድ አካባቢው እንደሚፈጸም ተገልጿል።
#ethiopia | ሳህለገብርኤል ይትባረክ አስከሬን ቤተሰቦቹ፣ ወዳጅ ዘመዶቹና የሥራ ባልደረቦቹ በተገኙበት በFederal Prison Commission የሽኝት ሥነ ሥርዓት ተካሂዶለታል።
በሥነ ሥርዓቱ ላይ የAddis Media Network እና የፌደራል ማረሚያ ቤት አመራሮች የአበባ ጉንጉን በማኖር ክብራቸውን ገልጸዋል።
ሳህለገብርኤል በጎጃም ቢቸና ተወልዶ ያደገ ሲሆን፣ በ18 ዓመቱ የፌደራል ማረሚያ ፖሊስን በመቀላቀል ከፖሊስ አባልነት እስከ ምክትል ኢንስፔክተርነት በታማኝነት አገልግሏል።
ከሙያው ጎን ለጎን የልጅነት ህልሙ የነበረውን የጋዜጠኝነት ሙያ በBahir Dar University በመማር የመጀመሪያ ዲግሪውን አግኝቶ በሙያው በትጋት ሲያገለግል ቆይቷል።
የሙያ ባልደረቦቹና አመራሮቹ ሳህለገብርኤል በትሕትናው፣ በሥራ ወዳድነቱ፣ በታማኝነቱና በመልካም ሥነ ምግባሩ የሚታወቅ እና ለብዙዎች አርአያ የነበረ ጋዜጠኛ እንደነበር አስታውሰዋል።
ሳህለገብርኤል ሰኔ 19 ቀን 2018 ዓ.ም. በድንገት ህይወቱ ያለፈ ሲሆን፣ ባለትዳርና የሦስት ልጆች አባት ነበር።
ሥርዓተ ቀብሩም በትውልድ አካባቢው እንደሚፈጸም ተገልጿል።
1 month ago
ጋዜጠኛ ሣህለገብርኤል ይትባረክ በድንገት ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ
ላለፉት 10 ዓመታት በአዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ በዜና አንባቢነት ያገለገለው ጋዜጠኛ ሣህለገብርኤል ይትባረክ በድንገት ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል።
ከጋዜጠኝነት ሙያው በተጨማሪ በማረሚያ ፖሊስ አባልነት እስከ ረዳት ኢንስፔክተርነት ማዕረግ የደረሰው ረዳት ኢንስፔክተር ሣህለገብርኤል፣ ሕይወቱ እስካለፈበት ዕለት ድረስ በፌዴራል ማረሚያ ቤቶች ኮሚሽን የሕዝብ ግንኙነት ክፍል የሚዲያ ማስተባበሪያ ኃላፊ በመሆን እያገለገለ ነበር።
በ18 ዓመቱ የማረሚያ ፖሊስን የተቀላቀለው ረዳት ኢንስፔክተር ሣህለገብርኤል ይትባረክ፣ ባለትዳርና የሦስት ልጆች አባት ነበር።
ላለፉት 10 ዓመታት በአዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ በዜና አንባቢነት ያገለገለው ጋዜጠኛ ሣህለገብርኤል ይትባረክ በድንገት ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል።
ከጋዜጠኝነት ሙያው በተጨማሪ በማረሚያ ፖሊስ አባልነት እስከ ረዳት ኢንስፔክተርነት ማዕረግ የደረሰው ረዳት ኢንስፔክተር ሣህለገብርኤል፣ ሕይወቱ እስካለፈበት ዕለት ድረስ በፌዴራል ማረሚያ ቤቶች ኮሚሽን የሕዝብ ግንኙነት ክፍል የሚዲያ ማስተባበሪያ ኃላፊ በመሆን እያገለገለ ነበር።
በ18 ዓመቱ የማረሚያ ፖሊስን የተቀላቀለው ረዳት ኢንስፔክተር ሣህለገብርኤል ይትባረክ፣ ባለትዳርና የሦስት ልጆች አባት ነበር።
1 month ago
ጋዜጠኛ ሣህለገብርኤል ይትባረክ በድንገት ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ
ሰኔ 19/2018 ዓ.ም
ከጋዜጠኝነት ሙያው በተጨማሪ በማረሚያ ፖሊስ አባልነት እስከ ረዳት ኢንስፔክተርነት ማዕረግ የደረሰው ረዳት ኢንስፔክተር ሣህለገብርኤል፣ ሕይወቱ እስካለፈበት ዕለት ድረስ በፌዴራል ማረሚያ ቤቶች ኮሚሽን የሕዝብ ግንኙነት ክፍል የሚዲያ ማስተባበሪያ ኃላፊ በመሆን እያገለገለ ነበር።
በ18 ዓመቱ የማረሚያ ፖሊስን የተቀላቀለው ረዳት ኢንስፔክተር ሣህለገብርኤል ይትባረክ፣ ባለትዳርና የሦስት ልጆች አባት ነበር።
በጋዜጠኛ ሣህለገብርኤል ይትባረክ ሕልፈት የተሰማንን ጥልቅ ሐዘን እየገለፅን፣ ለቤተሰቦቹ፣ ለሙያ አጋሮቹ እና ለወዳጅ ዘመዶቹ መጽናናትን እንመኛል።
የአብሥራ ተፈራ
Seledadotio
Seledadotio
ሰኔ 19/2018 ዓ.ም
ከጋዜጠኝነት ሙያው በተጨማሪ በማረሚያ ፖሊስ አባልነት እስከ ረዳት ኢንስፔክተርነት ማዕረግ የደረሰው ረዳት ኢንስፔክተር ሣህለገብርኤል፣ ሕይወቱ እስካለፈበት ዕለት ድረስ በፌዴራል ማረሚያ ቤቶች ኮሚሽን የሕዝብ ግንኙነት ክፍል የሚዲያ ማስተባበሪያ ኃላፊ በመሆን እያገለገለ ነበር።
በ18 ዓመቱ የማረሚያ ፖሊስን የተቀላቀለው ረዳት ኢንስፔክተር ሣህለገብርኤል ይትባረክ፣ ባለትዳርና የሦስት ልጆች አባት ነበር።
በጋዜጠኛ ሣህለገብርኤል ይትባረክ ሕልፈት የተሰማንን ጥልቅ ሐዘን እየገለፅን፣ ለቤተሰቦቹ፣ ለሙያ አጋሮቹ እና ለወዳጅ ዘመዶቹ መጽናናትን እንመኛል።
የአብሥራ ተፈራ
Seledadotio
Seledadotio
Sponsored by
Surafel
1 month ago
ብዙዎችን ያሳዘነው ዛሬ ጥዋት በድንገት ወድቆ የሞተው ጋዜጠኛ እና የህግ አስከባሪው ምክትል ኢንስፔክተር ሳህለገብርኤል ይትባረክ
በአዲስ አበባ ከተማ ዛሬ ጠዋት አንድ ከፍተኛ ሀዘን የፈጠረ ድንገተኛ ክስተት ተከስቷል። ታዋቂው ወጣት ጋዜጠኛ እና የፌዴራል ማረሚያ ቤቶች አገልግሎት ባልደረባ የሆነው ምክትል ኢንስፔክተር ሳህለገብርኤል ይትባረክ በድንገት ወድቆ ህይወቱ ማለፉ ተረጋግጧል።
ይህ ልብ ሰባሪ ዜና በባልደረቦቹ፣ በሙያ አጋሮቹ እና በሚያውቁት ማህበረሰብ ዘንድ ታላቅ ድንጋጤንና ሀዘንን ፈጥሯል።
ሟች ሳህለገብርኤል በአዲስ ቲቪ የዜና አንባቢ በመሆን ከማገልገሉ ባሻገር፣ በፌዴራል ማረሚያ ቤት በፖሊስ አባልነትና በምክትል ኢንስፔክተርነት ማዕረግ ሀገራዊ ግዳጁን በታማኝነት ሲወጣ የነበረ ታታሪ ወጣት ነበር።
ከበቸና ከተማ በመነሳት በዋና ከተማዋ የዜና ማዕከላትና በህግ ማስከበር ተቋማት ውስጥ የነበረው ተሳትፎ የብዙዎችን ትኩረት የሳበና ተስፋ የተጣለበት ነበር።
በስራ ቦታው ባሳየው መልካም ስነ-ምግባር፣ ዝቅታ እና እስረኞችን በሰብዓዊነት መንፈስ በመያዝ ረገድ በስራ ባልደረቦቹ ዘንድ እጅግ ተወዳጅና አርአያ የሚሆን ስብዕና ነበረው።
ሳህለገብርኤል ከዕረፍቱ ጥቂት ቀናት ቀደም ብሎ በማህበራዊ ትስስር ገጹ ላይ ያጋራው ፅሁፍ፣ ለሙያው ያለውን ጥልቅ ፍቅር እና ለወደፊት የነበረውን ትልቅ የሪፎርም ራዕይ በግልፅ ያሳያል።
በወቅቱ ባሰፈረው መልዕክት፣ በማረሚያ ቤት የፖሊስነት ህይወቱ በጣም ደስተኛ እንደነበረና የልጅነት ህልሙ የሆነውን የጋዜጠኝነትና የመሪነት ትምህርቱን እንዲማር እንዳስቻለው ገልጾ ነበር።
በተጨማሪም ፈጣሪ እድሜና ጤና ከሰጠው ማረሚያ ቤት እንዲሆን የሚፈልገውን ያህል ለማድረግ በግሉ መጣሩን እንደማያቆም በፅሁፉ አስፍሮ ነበር።
ይህ መልዕክት ዛሬ ከደረሰው አሳዛኝ መርዶ ጋር ተዳምሮ የብዙዎችን ልብ በሀዘን ሰብሯል።
የጋዜጠኛ ሳህለገብርኤል ይትባረክ ህልፈት በአጭር የተቀጨ ታላቅ ተስፋ ነው። የእርሱ መልካም ስራ፣ ሰብዓዊነት እና የፅናት አርአያነት ሁልጊዜም በብዙዎች ልብ ውስጥ ሲታወስ ይኖራል።
ለሟች ቤተሰቦች፣ የቅርብ ወዳጆች፣ የአዲስ ቲቪ እና የፌዴራል ማረሚያ ቤት የስራ ባልደረቦች እንዲሁም መላው ወዳጆቹ ፈጣሪ መፅናናትን እንዲሰጥ በጥልቅ እንመኛለን።
ነፍሱን በገነት ያኑርልን።
©️መረጃ ቲዩብ
በአዲስ አበባ ከተማ ዛሬ ጠዋት አንድ ከፍተኛ ሀዘን የፈጠረ ድንገተኛ ክስተት ተከስቷል። ታዋቂው ወጣት ጋዜጠኛ እና የፌዴራል ማረሚያ ቤቶች አገልግሎት ባልደረባ የሆነው ምክትል ኢንስፔክተር ሳህለገብርኤል ይትባረክ በድንገት ወድቆ ህይወቱ ማለፉ ተረጋግጧል።
ይህ ልብ ሰባሪ ዜና በባልደረቦቹ፣ በሙያ አጋሮቹ እና በሚያውቁት ማህበረሰብ ዘንድ ታላቅ ድንጋጤንና ሀዘንን ፈጥሯል።
ሟች ሳህለገብርኤል በአዲስ ቲቪ የዜና አንባቢ በመሆን ከማገልገሉ ባሻገር፣ በፌዴራል ማረሚያ ቤት በፖሊስ አባልነትና በምክትል ኢንስፔክተርነት ማዕረግ ሀገራዊ ግዳጁን በታማኝነት ሲወጣ የነበረ ታታሪ ወጣት ነበር።
ከበቸና ከተማ በመነሳት በዋና ከተማዋ የዜና ማዕከላትና በህግ ማስከበር ተቋማት ውስጥ የነበረው ተሳትፎ የብዙዎችን ትኩረት የሳበና ተስፋ የተጣለበት ነበር።
በስራ ቦታው ባሳየው መልካም ስነ-ምግባር፣ ዝቅታ እና እስረኞችን በሰብዓዊነት መንፈስ በመያዝ ረገድ በስራ ባልደረቦቹ ዘንድ እጅግ ተወዳጅና አርአያ የሚሆን ስብዕና ነበረው።
ሳህለገብርኤል ከዕረፍቱ ጥቂት ቀናት ቀደም ብሎ በማህበራዊ ትስስር ገጹ ላይ ያጋራው ፅሁፍ፣ ለሙያው ያለውን ጥልቅ ፍቅር እና ለወደፊት የነበረውን ትልቅ የሪፎርም ራዕይ በግልፅ ያሳያል።
በወቅቱ ባሰፈረው መልዕክት፣ በማረሚያ ቤት የፖሊስነት ህይወቱ በጣም ደስተኛ እንደነበረና የልጅነት ህልሙ የሆነውን የጋዜጠኝነትና የመሪነት ትምህርቱን እንዲማር እንዳስቻለው ገልጾ ነበር።
በተጨማሪም ፈጣሪ እድሜና ጤና ከሰጠው ማረሚያ ቤት እንዲሆን የሚፈልገውን ያህል ለማድረግ በግሉ መጣሩን እንደማያቆም በፅሁፉ አስፍሮ ነበር።
ይህ መልዕክት ዛሬ ከደረሰው አሳዛኝ መርዶ ጋር ተዳምሮ የብዙዎችን ልብ በሀዘን ሰብሯል።
የጋዜጠኛ ሳህለገብርኤል ይትባረክ ህልፈት በአጭር የተቀጨ ታላቅ ተስፋ ነው። የእርሱ መልካም ስራ፣ ሰብዓዊነት እና የፅናት አርአያነት ሁልጊዜም በብዙዎች ልብ ውስጥ ሲታወስ ይኖራል።
ለሟች ቤተሰቦች፣ የቅርብ ወዳጆች፣ የአዲስ ቲቪ እና የፌዴራል ማረሚያ ቤት የስራ ባልደረቦች እንዲሁም መላው ወዳጆቹ ፈጣሪ መፅናናትን እንዲሰጥ በጥልቅ እንመኛለን።
ነፍሱን በገነት ያኑርልን።
©️መረጃ ቲዩብ
2 months ago
ኮሚሽኑ ለሀገራዊ ምክክር ጉባኤው የመገናኛ ብዙኃን የንቅናቄ ዘመቻ አስጀመረ
*************
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን የሀገራዊ ምክክር ጉባኤውን ለማሳካት የሚያስችል የንቅናቄ ዘመቻ ለመጀመር በኢትዮጵያ ከሚገኙ የመገናኛ ብዙኃን ተቋማት ኃላፊዎችና ከፍተኛ ባለሞያዎች ጋር ውይይት አካሂዷል።
በውይይቱ የኮሚሽኑ ኮሚሽነር አምባሳደር መሀሙድ ድሪር፣ ኮሚሽነር መላኩ ወ/ማርያም እና ኮሚሽነር ዮናስ አዳዬ (ዶ/ር) መገናኛ ብዙሀን ከኮሚሽኑ ጋር በመስራት እስካሁን ላበረከቱት አስተዋፅኦ ምስጋና አቅርበዋል።
ቀጣዩ ሀገራዊ ጉባኤ ከቅድመ ጉባኤ ጀምሮ ጥንቃቄ የተሞላበት የአዘጋገብ ስልት ስለሚጠይቅ ይህንን ለማስገንዘብ እና ሰፊ የግንዛቤ ማስጨበጫ ዘመቻ ለመጀመር መድረኩ መዘጋጀቱን አክለዋል።
መገናኛ ብዙሀን የሀገራዊ ምክክሩን ሂደት ሲዘግቡ በአካታችነት መርሁ መሰረት የሁሉንም ዜጎች ድምፅ በማካተትት፣ የኮሚሽኑን ነፃና ገለልተኛ አሰራር በመጠበቅ እንዲሁም ዘላቂ ሰላምና መግባባት ለመፍጠር በሚያግዝ መልኩ መሆኑን እንዳለበት ነው አፅንኦት ሰጥተው ያስገነዘቡት።
ከቅድመ ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ እስከ ድህረ ጉባኤ መገናኛ ብዙኃን ትክክለኛ፣ ሚዛናዊ እና ተደራሽ መረጃ በማቅረብ ሚናቸውን እንዲወጡም አክለዋል።
በመድረኩ የመወያያ ፅሁፍ ያቀረቡት በአዲስ አበባ ዩንቨርስቲ የጋዜጠኝነትና ኮሙኒኬሽን ትምህርት ክፍል ሀላፊ ዮሀንስ ሽፈራው (ዶ/ር) ዓለም አቀፍ ተሞክሮዎችን በመጥቀስ ሀገራዊ የምክክር ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን መገናኛ ብዙሀን ሊከተሏቸው የሚገቡ የአዘጋገብ ስልቶችና ሙያዊ ስነምግባሮችን አመላክተዋል።
የመገናኛ ብዙኃን ኃላፊዎች በበኩላቸው የሀገራዊ ምክክር ሂደቱን ለሕዝብ በስፋት ለማስተዋወቅና በሂደቱ ዙሪያ የሚቀርቡ መረጃዎች ተዓማኒነት እንዲኖራቸው በትኩረት እንደሚሰሩ መግለጻቸውን የኮሚሽኑ መረጃ ያመላክታል።
በዕለቱ ኮሚሽኑ በራሱ የውስጥ አቅም ያዘጋጃቸውን 15 የክልል የምክክር መድረክ ዘጋቢ ፊልሞች፣ 19 የቴሌቪዥንና የማህበራዊ ሚዲያ የቅስቀሳ መልዕክቶችን፣ 6 የሬዲዮ መልዕክቶችን እንዲሁም በልዩ ልዩ ቋንቋዎች የተዘጋጁ አጫጫር መልዕክቶችን ለሚዲያ አመራሮቹ አስረክቧል።
ኮሚሽኑ ያስረከባቸው መልዕክቶች መገናኛ ብዙኃኑ በራሳቸው አቅም ከሚያዘጋጇቸው ተጨማሪ ሆነው እንደ ግብዓት እንደሚያገለግሉ ተነግሯል።
መልዕክቶቹን ከመጪው ሰኞ ሰኔ 15/2018 ዓ.ም ጀምሮ በስፋት ወደ ሕዝብ ለማድረስ በኮሚሽኑና በመገናኛ ብዙሀኑ መካከል መግባባት ላይ ተደርሷል።
በዚህ የንቅናቄ ማስጀመሪያ መድረክ ከ80 በላይ የቴሌቪዥን፣ የሬዲዮና የሕትመት ሚዲያ አመራሮችና ከፍተኛ ባለሞያዎች እንዲሁም የኢትዮ ቴሌኮሚ፣ የትምህርት፣ የጤና እና የትራንስፓርትና ሎጂስቲክስ ዘርፍ የኮሙኒኬሽን ሀላፊዎች እና የተለያዩ የክብር እንግዶች ተሳትፈዋል።
ኮሚሽኑ ባለፈው ሳምንት በመላ ሀገሪቱ የሚገኙ 50 የማህበረሰብ መገናኛ ብዙሀን ሀላፊዎችንና ባለሙያዎችን ያገኘበት መድረክ አከናውኖ ተመሳሳይ የሚዲያ ንቅናቄ ዘመቻ ማስጀመሩ ይታወሳል።
#ethiopianbroadcastingcorporation #ethiopiannationaldialoguecommission #nationaldialogue #mediacampaign #peaceandunity
*************
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን የሀገራዊ ምክክር ጉባኤውን ለማሳካት የሚያስችል የንቅናቄ ዘመቻ ለመጀመር በኢትዮጵያ ከሚገኙ የመገናኛ ብዙኃን ተቋማት ኃላፊዎችና ከፍተኛ ባለሞያዎች ጋር ውይይት አካሂዷል።
በውይይቱ የኮሚሽኑ ኮሚሽነር አምባሳደር መሀሙድ ድሪር፣ ኮሚሽነር መላኩ ወ/ማርያም እና ኮሚሽነር ዮናስ አዳዬ (ዶ/ር) መገናኛ ብዙሀን ከኮሚሽኑ ጋር በመስራት እስካሁን ላበረከቱት አስተዋፅኦ ምስጋና አቅርበዋል።
ቀጣዩ ሀገራዊ ጉባኤ ከቅድመ ጉባኤ ጀምሮ ጥንቃቄ የተሞላበት የአዘጋገብ ስልት ስለሚጠይቅ ይህንን ለማስገንዘብ እና ሰፊ የግንዛቤ ማስጨበጫ ዘመቻ ለመጀመር መድረኩ መዘጋጀቱን አክለዋል።
መገናኛ ብዙሀን የሀገራዊ ምክክሩን ሂደት ሲዘግቡ በአካታችነት መርሁ መሰረት የሁሉንም ዜጎች ድምፅ በማካተትት፣ የኮሚሽኑን ነፃና ገለልተኛ አሰራር በመጠበቅ እንዲሁም ዘላቂ ሰላምና መግባባት ለመፍጠር በሚያግዝ መልኩ መሆኑን እንዳለበት ነው አፅንኦት ሰጥተው ያስገነዘቡት።
ከቅድመ ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ እስከ ድህረ ጉባኤ መገናኛ ብዙኃን ትክክለኛ፣ ሚዛናዊ እና ተደራሽ መረጃ በማቅረብ ሚናቸውን እንዲወጡም አክለዋል።
በመድረኩ የመወያያ ፅሁፍ ያቀረቡት በአዲስ አበባ ዩንቨርስቲ የጋዜጠኝነትና ኮሙኒኬሽን ትምህርት ክፍል ሀላፊ ዮሀንስ ሽፈራው (ዶ/ር) ዓለም አቀፍ ተሞክሮዎችን በመጥቀስ ሀገራዊ የምክክር ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን መገናኛ ብዙሀን ሊከተሏቸው የሚገቡ የአዘጋገብ ስልቶችና ሙያዊ ስነምግባሮችን አመላክተዋል።
የመገናኛ ብዙኃን ኃላፊዎች በበኩላቸው የሀገራዊ ምክክር ሂደቱን ለሕዝብ በስፋት ለማስተዋወቅና በሂደቱ ዙሪያ የሚቀርቡ መረጃዎች ተዓማኒነት እንዲኖራቸው በትኩረት እንደሚሰሩ መግለጻቸውን የኮሚሽኑ መረጃ ያመላክታል።
በዕለቱ ኮሚሽኑ በራሱ የውስጥ አቅም ያዘጋጃቸውን 15 የክልል የምክክር መድረክ ዘጋቢ ፊልሞች፣ 19 የቴሌቪዥንና የማህበራዊ ሚዲያ የቅስቀሳ መልዕክቶችን፣ 6 የሬዲዮ መልዕክቶችን እንዲሁም በልዩ ልዩ ቋንቋዎች የተዘጋጁ አጫጫር መልዕክቶችን ለሚዲያ አመራሮቹ አስረክቧል።
ኮሚሽኑ ያስረከባቸው መልዕክቶች መገናኛ ብዙኃኑ በራሳቸው አቅም ከሚያዘጋጇቸው ተጨማሪ ሆነው እንደ ግብዓት እንደሚያገለግሉ ተነግሯል።
መልዕክቶቹን ከመጪው ሰኞ ሰኔ 15/2018 ዓ.ም ጀምሮ በስፋት ወደ ሕዝብ ለማድረስ በኮሚሽኑና በመገናኛ ብዙሀኑ መካከል መግባባት ላይ ተደርሷል።
በዚህ የንቅናቄ ማስጀመሪያ መድረክ ከ80 በላይ የቴሌቪዥን፣ የሬዲዮና የሕትመት ሚዲያ አመራሮችና ከፍተኛ ባለሞያዎች እንዲሁም የኢትዮ ቴሌኮሚ፣ የትምህርት፣ የጤና እና የትራንስፓርትና ሎጂስቲክስ ዘርፍ የኮሙኒኬሽን ሀላፊዎች እና የተለያዩ የክብር እንግዶች ተሳትፈዋል።
ኮሚሽኑ ባለፈው ሳምንት በመላ ሀገሪቱ የሚገኙ 50 የማህበረሰብ መገናኛ ብዙሀን ሀላፊዎችንና ባለሙያዎችን ያገኘበት መድረክ አከናውኖ ተመሳሳይ የሚዲያ ንቅናቄ ዘመቻ ማስጀመሩ ይታወሳል።
#ethiopianbroadcastingcorporation #ethiopiannationaldialoguecommission #nationaldialogue #mediacampaign #peaceandunity
2 months ago
ሐሳብን በነጻነት የመግለጽ መብት እና የሕግ የበላይነት!!
መግቢያ፤
በማንኛውም ዴሞክራሲያዊ ማኅበረሰብ ውስጥ ሐሳብን በነጻነት የመግለጽ መብት እና የፕሬስ ነጻነት የሉዓላዊነትና የነጻነት መገለጫዎች ተደርገው ይወሰዳሉ። በተለይም በመገናኛ ብዙኃን የሚሠሩ ጋዜጠኞች የማኅበረሰቡን ድምፅ በማስተጋባት፣ የመንግሥትን አሠራር በመታዘብና ተጠያቂነትን በማስፈን ረገድ የጎላ ሚና አላቸው።
ይሁን እንጂ የፕሬስ ነጻነትና የብሔራዊ ደኅንነት ሚዛን፣ እንዲሁም በመንግሥት ጸጥታ ኃይሎች የሚወሰዱ እርምጃዎች ከሕገ-መንግሥታዊ ድንጋጌዎች ጋር ያላቸው መጣጣም በተደጋጋሚ ለክርክር የሚዳርግ ጉዳይ ነው።
ይህ ጽሑፍ ማንነትንና ሃይማኖትን ማእከል ባደረጉ ግድያዎችና ማፈናቀሎች ዙሪያ በሠራቻቸው ቪዲዮዎች ከሰሞኑን በቁጥጥር ስር የዋለችውንና ለ10 ቀናት ፍርድ ቤት ያልቀረበችውን የጋዜጠኛ ሣልሳዊት ባይነሳኝ ጉዳይ መነሻ በማድረግ- የኢትዮጵያን ሕገ-መንግሥት እና ዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብቶች ስምምነቶችን መሠረት በማድረግ ሙግታዊ ትንታኔ ያቀርባል።
1. ሐሳብን በነጻነት የመግለጽ መብት ሕገ-መንግሥታዊና ዓለም አቀፋዊ መሠረቶች፤
የኢፌድሪ ሕገ-መንግሥት በአንቀጽ ፳፱ (29) ላይ ማንኛውም ሰው ያለ ምንም ጣልቃ ገብነት የፈለገውን ሐሳብ የመያዝ፣ የመግለጽና መረጃ የመሰብሰብ እንዲሁም የማሰራጨት መብት እንዳለው በግልጽ ይደነግጋል። ይህ መብት በተለይ የፕሬስ ነጻነትንና የሚዲያ ተቋማትን ሥራ የሚመለከት ሲሆን ሳንሱር በሕግ የተከለከለ መሆኑንም ያረጋግጣል።
ከዚህ በተጨማሪ ኢትዮጵያ ተቀብላ ያጸደቀቻቸው ዓለም አቀፍ ስምምነቶች ለምሳሌ፤
የዓለም አቀፍ የሲቪልና የፖለቲካ መብቶች ቃል ኪዳን (ICCPR) አንቀጽ 19፤
የአፍሪካ የሰዎችና የሕዝቦች መብቶች ቻርተር (ACHPR) አንቀጽ 9፤
እነዚህ ሰነዶች ሐሳብን የመግለጽ ነጻነት የሰብአዊ መብቶች ሁሉ መሠረት መሆኑን ያስገነዝባሉ። ከንድፈ-ሐሳብ አንጻር እንደ John Stuart Mill ያሉ ምሁራን፤ "የሐሳብ የገበያ ቦታ" (Marketplace of Ideas) በሚለው እሳቤያቸው፤ እውነት ሊገኝ የሚችለው ሐሳቦች በነጻነት ሲንሸራሸሩና ክርክር ሲደረግባቸው ብቻ እንደሆነ ይከራከራሉ።
በመሆኑም ጋዜጠኞች በማኅበረሰቡ ውስጥ ያሉ አስከፊ እውነታዎችን (እንደ ማፈናቀልና ግድያ ያሉ) ይፋ ማድረጋቸው የሙያዊ ኃላፊነትና የሕዝብን መረጃ የማግኘት መብት የማክበር ጉዳይ ተደርጎ ሊወሰድ ይገባል።
2. የፍጹምነት ወሰን እና የብሔራዊ ደኅንነት ሚዛን፤
ምንም እንኳን ሐሳብን በነጻነት የመግለጽ መብት መሠረታዊ ቢሆንም ፍጹም (Absolute) አይደለም። የኢፌድሪ ሕገ-መንግሥት አንቀጽ 29(6) እንዲሁም የ-ICCPR አንቀጽ 19(3) መብቱ ገደብ ሊጣልበት የሚችልባቸውን ሁኔታዎች ያስቀምጣሉ።
እነዚህም የሌሎችን መብትና ክብር ለመጠበቅ፤
ብሔራዊ ደኅንነትን፣ የሕዝብን ሰላምና ጸጥታን እንዲሁም የሕዝብን ጤና ወይም ሥነ-ምግባር ለመጠበቅ ሲባል ነው።
የሙግት ነጥብ፡- በሀገሪቱ ስሱ የሆኑ የማንነትና የሃይማኖት ጉዳዮችን ይፋዊ የቪዲዮ ምስሎችንና ጽሑፎችን ማጋራት በአንድ በኩል ግልጽነትንና እውነትን ማውጣትን የሚያበረታታ ሲሆን፤ በሌላ በኩል ደግሞ ይዘቶቹ የጥላቻ ንግግርን (Hate Speech) የሚያነሳሱ፣ ወይም ግጭትን የሚቀሰቅሱ ከሆኑ በሕግ ሊጠየቁ የሚችሉበት ዕድል አለ።
ሆኖም ግን ይህ ገደብ ሥራ ላይ ሊውል የሚችለው በሕግ የተደነገገ (Prescribed by Law) አስፈላጊ (Necessary) እና ተመጣጣኝ (Proportional) በሆነ መንገድ ብቻ መሆን እንዳለበት የሰብአዊ መብት ተሟጋቾችና ምሁራን ይከራከራሉ። ጋዜጠኛን ማሰር የመጨረሻ አማራጭ (Ultima Ratio) መሆን ያለበት እንጂ የዜጎችን የመረጃ ፍሰት መግቻ መሣሪያ መሆን የለበትም።
3. የ48 ሰዓት ሕገ-መንግሥታዊ ግዴታ እና የሕግ የበላይነት መሸርሸር፤
የዚህ ጉዳይ ዋነኛውና አሳሳቢው ሕጋዊ ጥሰት የሚጀምረው ጋዜጠኛዋ በቁጥጥር ስር ከዋለች በኋላ ከተፈጸመው የአያያዝ ሂደት ነው። የኢፌድሪ ሕገ-መንግሥት አንቀጽ ፲፱ (፫) በግልጽ እንደሚያስቀምጠው፦
"የተያዙ ሰዎች በቁጥጥር ስር በዋሉ በ48 ሰዓት ውስጥ ፍርድ ቤት የመቅረብ መብት አላቸው። ይህ ጊዜ ተያዙበት ቦታ ወደ ፍርድ ቤት ለመምጣት ከሚያስፈልገው ተገቢ ጊዜን አይጨምርም ነፃነታቸውን እንዳያጡ ለመከላከል ወዲያውኑ ፍርድ ቤት የመቅረብ መብት አላቸው።"
ይህ ድንጋጌ የፓርላማ ሕግ ሳይሆን፣ የሀገሪቱ የበላይ ሕግ (Supreme Law) ነው። ጋዜጠኛዋ ላለፉት 10 ቀናት ፍርድ ቤት ሳትቀርብ መቅረቷ ይህንን ሕገ-መንግሥታዊ መሠረት በግልጽ የጣሰ ድርጊት ነው።
ምሁራዊና ተጠየቃዊ ትንታኔ (Theoretic and Philosophical Perspective)፤
ሐቤስ ኮርፐስ (Habeas Corpus)፦ ይህ መርህ በሕግ ታሪክ ውስጥ ግብረ-ገብነትንና ፍትሕን ለማስፈን ከተቀረጹ ትልልቅ መርሆዎች አንዱ ነው። ትርጉሙም "አካሉን ይዘህ ቅረብ" ማለት ሲሆን አስፈጻሚው አካል (የጸጥታ ኃይሉ) አንድን ዜጋ ያለ ፍርድ ቤት ትዕዛዝ ለረጅም ጊዜ አፍኖ እንዳያቆይ የሚከላከል የነጻነት ጋሻ ነው።
የሥልጣን ክፍፍል መርህ (Separation of Powers)፦ በቻርለስ ደ ሞንቴስኪው (Montesquieu) ፍልስፍና መሠረት፣ የሕግ አስፈጻሚው አካል (ፖሊስ/ጸጥታ) ሰዎችን የመያዝ ሥልጣን ቢኖረውም የእስሩን ሕጋዊነት የመመርመርና የመወሰን ሥልጣን ሙሉ በሙሉ የሕግ ተርጓሚው (የፍርድ ቤት) ብቻ ነው።
ፖሊስ አንድን ዜጋ ለ10 ቀናት ፍርድ ቤት ሳይልክ ሲያቆይ ራሱን በሕግ ተርጓሚነት ቦታ ላይ እየሰየመ መሆኑን ያሳያል። ይህ ደግሞ ወደ አምባገንነትና ወደ ሕግ አልባነት (Arbitrary Detention) የሚወስድ አደገኛ መንገድ ነው።
የጸጥታ ኃይሎች የሚዲያ ይዘቱ "የሀገር ደኅንነትን ይነካል" የሚል እምነት ቢኖራቸው እንኳ ያንን እምነታቸውንና ያሏቸውን ማስረጃዎች በ48 ሰዓት ውስጥ ለገለልተኛ ዳኛ አቅርበው የተጨማሪ ምርመራ ጊዜ (Remand) መጠየቅ ነበረባቸው። ይህ ሳይሆን መቅረቱ የእስሩን ሕጋዊነት ሙሉ በሙሉ ጥያቄ ውስጥ የሚጥለውና የመንግሥትን ሕግ የማክበር ግዴታ (Duty to Respect) የሚሸረሽር ነው።
መደምደሚያ፤
ጋዜጠኝነት ወንጀል አይደለም ይልቁንም የማኅበረሰብን ሕመም የሚያሳይ መስተዋት ነው። በማንነትና በሃይማኖት ላይ የሚፈጸሙ ግድያዎችንና መፈናቀሎችን ወደ አደባባይ ማውጣት፣ መንግሥት ኃላፊነቱን እንዲወጣ የሚያስገድድ የሕዝብ ድምፅ ሊሆን ይችላል።
የይዘቱ አግባብነትና ሕጋዊነት ጥያቄ ውስጥ የሚወድቅ ቢሆን እንኳ ሊፈታ የሚገባው በሕገ-መንግሥታዊና በሕጋዊ ሥርዓቶች መዋቅር ውስጥ ብቻ ነው።
አንድን ጋዜጠኛ ለ10 ቀናት ያለ ፍርድ ቤት ትዕዛዝ ማሰር ሕገ-መንግሥቱን መጣስ ብቻ ሳይሆን፣ በሀገሪቱ የዲሞክራሲ ምኅዳር ላይ የፍርሃት ጥላ (Chilling Effect) የሚያሳድር ድርጊት ነው።
መንግሥት የሕግ የበላይነትን ለማስከበር መጀመሪያ ራሱ በሕግ መገዛት አለበት። ስለሆነም ጋዜጠኛዋ በአስቸኳይ ፍርድ ቤት ልትቀርብ ወይም ሕገ-መንግሥታዊ መብቷ ተከብሮ በአፋጣኝ ልትፈታ ይገባል።
ሕግን ለመጠበቅ በሚደረግ ጉዞ ውስጥ ሕግን መጣስ፣ ራሱ ሌላ የሕግ መፍረስን የሚወልድ በመሆኑ ሥርዓቱ ሊታረም ይገባዋል።
(በፍቅር ለይኩን)፤
መግቢያ፤
በማንኛውም ዴሞክራሲያዊ ማኅበረሰብ ውስጥ ሐሳብን በነጻነት የመግለጽ መብት እና የፕሬስ ነጻነት የሉዓላዊነትና የነጻነት መገለጫዎች ተደርገው ይወሰዳሉ። በተለይም በመገናኛ ብዙኃን የሚሠሩ ጋዜጠኞች የማኅበረሰቡን ድምፅ በማስተጋባት፣ የመንግሥትን አሠራር በመታዘብና ተጠያቂነትን በማስፈን ረገድ የጎላ ሚና አላቸው።
ይሁን እንጂ የፕሬስ ነጻነትና የብሔራዊ ደኅንነት ሚዛን፣ እንዲሁም በመንግሥት ጸጥታ ኃይሎች የሚወሰዱ እርምጃዎች ከሕገ-መንግሥታዊ ድንጋጌዎች ጋር ያላቸው መጣጣም በተደጋጋሚ ለክርክር የሚዳርግ ጉዳይ ነው።
ይህ ጽሑፍ ማንነትንና ሃይማኖትን ማእከል ባደረጉ ግድያዎችና ማፈናቀሎች ዙሪያ በሠራቻቸው ቪዲዮዎች ከሰሞኑን በቁጥጥር ስር የዋለችውንና ለ10 ቀናት ፍርድ ቤት ያልቀረበችውን የጋዜጠኛ ሣልሳዊት ባይነሳኝ ጉዳይ መነሻ በማድረግ- የኢትዮጵያን ሕገ-መንግሥት እና ዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብቶች ስምምነቶችን መሠረት በማድረግ ሙግታዊ ትንታኔ ያቀርባል።
1. ሐሳብን በነጻነት የመግለጽ መብት ሕገ-መንግሥታዊና ዓለም አቀፋዊ መሠረቶች፤
የኢፌድሪ ሕገ-መንግሥት በአንቀጽ ፳፱ (29) ላይ ማንኛውም ሰው ያለ ምንም ጣልቃ ገብነት የፈለገውን ሐሳብ የመያዝ፣ የመግለጽና መረጃ የመሰብሰብ እንዲሁም የማሰራጨት መብት እንዳለው በግልጽ ይደነግጋል። ይህ መብት በተለይ የፕሬስ ነጻነትንና የሚዲያ ተቋማትን ሥራ የሚመለከት ሲሆን ሳንሱር በሕግ የተከለከለ መሆኑንም ያረጋግጣል።
ከዚህ በተጨማሪ ኢትዮጵያ ተቀብላ ያጸደቀቻቸው ዓለም አቀፍ ስምምነቶች ለምሳሌ፤
የዓለም አቀፍ የሲቪልና የፖለቲካ መብቶች ቃል ኪዳን (ICCPR) አንቀጽ 19፤
የአፍሪካ የሰዎችና የሕዝቦች መብቶች ቻርተር (ACHPR) አንቀጽ 9፤
እነዚህ ሰነዶች ሐሳብን የመግለጽ ነጻነት የሰብአዊ መብቶች ሁሉ መሠረት መሆኑን ያስገነዝባሉ። ከንድፈ-ሐሳብ አንጻር እንደ John Stuart Mill ያሉ ምሁራን፤ "የሐሳብ የገበያ ቦታ" (Marketplace of Ideas) በሚለው እሳቤያቸው፤ እውነት ሊገኝ የሚችለው ሐሳቦች በነጻነት ሲንሸራሸሩና ክርክር ሲደረግባቸው ብቻ እንደሆነ ይከራከራሉ።
በመሆኑም ጋዜጠኞች በማኅበረሰቡ ውስጥ ያሉ አስከፊ እውነታዎችን (እንደ ማፈናቀልና ግድያ ያሉ) ይፋ ማድረጋቸው የሙያዊ ኃላፊነትና የሕዝብን መረጃ የማግኘት መብት የማክበር ጉዳይ ተደርጎ ሊወሰድ ይገባል።
2. የፍጹምነት ወሰን እና የብሔራዊ ደኅንነት ሚዛን፤
ምንም እንኳን ሐሳብን በነጻነት የመግለጽ መብት መሠረታዊ ቢሆንም ፍጹም (Absolute) አይደለም። የኢፌድሪ ሕገ-መንግሥት አንቀጽ 29(6) እንዲሁም የ-ICCPR አንቀጽ 19(3) መብቱ ገደብ ሊጣልበት የሚችልባቸውን ሁኔታዎች ያስቀምጣሉ።
እነዚህም የሌሎችን መብትና ክብር ለመጠበቅ፤
ብሔራዊ ደኅንነትን፣ የሕዝብን ሰላምና ጸጥታን እንዲሁም የሕዝብን ጤና ወይም ሥነ-ምግባር ለመጠበቅ ሲባል ነው።
የሙግት ነጥብ፡- በሀገሪቱ ስሱ የሆኑ የማንነትና የሃይማኖት ጉዳዮችን ይፋዊ የቪዲዮ ምስሎችንና ጽሑፎችን ማጋራት በአንድ በኩል ግልጽነትንና እውነትን ማውጣትን የሚያበረታታ ሲሆን፤ በሌላ በኩል ደግሞ ይዘቶቹ የጥላቻ ንግግርን (Hate Speech) የሚያነሳሱ፣ ወይም ግጭትን የሚቀሰቅሱ ከሆኑ በሕግ ሊጠየቁ የሚችሉበት ዕድል አለ።
ሆኖም ግን ይህ ገደብ ሥራ ላይ ሊውል የሚችለው በሕግ የተደነገገ (Prescribed by Law) አስፈላጊ (Necessary) እና ተመጣጣኝ (Proportional) በሆነ መንገድ ብቻ መሆን እንዳለበት የሰብአዊ መብት ተሟጋቾችና ምሁራን ይከራከራሉ። ጋዜጠኛን ማሰር የመጨረሻ አማራጭ (Ultima Ratio) መሆን ያለበት እንጂ የዜጎችን የመረጃ ፍሰት መግቻ መሣሪያ መሆን የለበትም።
3. የ48 ሰዓት ሕገ-መንግሥታዊ ግዴታ እና የሕግ የበላይነት መሸርሸር፤
የዚህ ጉዳይ ዋነኛውና አሳሳቢው ሕጋዊ ጥሰት የሚጀምረው ጋዜጠኛዋ በቁጥጥር ስር ከዋለች በኋላ ከተፈጸመው የአያያዝ ሂደት ነው። የኢፌድሪ ሕገ-መንግሥት አንቀጽ ፲፱ (፫) በግልጽ እንደሚያስቀምጠው፦
"የተያዙ ሰዎች በቁጥጥር ስር በዋሉ በ48 ሰዓት ውስጥ ፍርድ ቤት የመቅረብ መብት አላቸው። ይህ ጊዜ ተያዙበት ቦታ ወደ ፍርድ ቤት ለመምጣት ከሚያስፈልገው ተገቢ ጊዜን አይጨምርም ነፃነታቸውን እንዳያጡ ለመከላከል ወዲያውኑ ፍርድ ቤት የመቅረብ መብት አላቸው።"
ይህ ድንጋጌ የፓርላማ ሕግ ሳይሆን፣ የሀገሪቱ የበላይ ሕግ (Supreme Law) ነው። ጋዜጠኛዋ ላለፉት 10 ቀናት ፍርድ ቤት ሳትቀርብ መቅረቷ ይህንን ሕገ-መንግሥታዊ መሠረት በግልጽ የጣሰ ድርጊት ነው።
ምሁራዊና ተጠየቃዊ ትንታኔ (Theoretic and Philosophical Perspective)፤
ሐቤስ ኮርፐስ (Habeas Corpus)፦ ይህ መርህ በሕግ ታሪክ ውስጥ ግብረ-ገብነትንና ፍትሕን ለማስፈን ከተቀረጹ ትልልቅ መርሆዎች አንዱ ነው። ትርጉሙም "አካሉን ይዘህ ቅረብ" ማለት ሲሆን አስፈጻሚው አካል (የጸጥታ ኃይሉ) አንድን ዜጋ ያለ ፍርድ ቤት ትዕዛዝ ለረጅም ጊዜ አፍኖ እንዳያቆይ የሚከላከል የነጻነት ጋሻ ነው።
የሥልጣን ክፍፍል መርህ (Separation of Powers)፦ በቻርለስ ደ ሞንቴስኪው (Montesquieu) ፍልስፍና መሠረት፣ የሕግ አስፈጻሚው አካል (ፖሊስ/ጸጥታ) ሰዎችን የመያዝ ሥልጣን ቢኖረውም የእስሩን ሕጋዊነት የመመርመርና የመወሰን ሥልጣን ሙሉ በሙሉ የሕግ ተርጓሚው (የፍርድ ቤት) ብቻ ነው።
ፖሊስ አንድን ዜጋ ለ10 ቀናት ፍርድ ቤት ሳይልክ ሲያቆይ ራሱን በሕግ ተርጓሚነት ቦታ ላይ እየሰየመ መሆኑን ያሳያል። ይህ ደግሞ ወደ አምባገንነትና ወደ ሕግ አልባነት (Arbitrary Detention) የሚወስድ አደገኛ መንገድ ነው።
የጸጥታ ኃይሎች የሚዲያ ይዘቱ "የሀገር ደኅንነትን ይነካል" የሚል እምነት ቢኖራቸው እንኳ ያንን እምነታቸውንና ያሏቸውን ማስረጃዎች በ48 ሰዓት ውስጥ ለገለልተኛ ዳኛ አቅርበው የተጨማሪ ምርመራ ጊዜ (Remand) መጠየቅ ነበረባቸው። ይህ ሳይሆን መቅረቱ የእስሩን ሕጋዊነት ሙሉ በሙሉ ጥያቄ ውስጥ የሚጥለውና የመንግሥትን ሕግ የማክበር ግዴታ (Duty to Respect) የሚሸረሽር ነው።
መደምደሚያ፤
ጋዜጠኝነት ወንጀል አይደለም ይልቁንም የማኅበረሰብን ሕመም የሚያሳይ መስተዋት ነው። በማንነትና በሃይማኖት ላይ የሚፈጸሙ ግድያዎችንና መፈናቀሎችን ወደ አደባባይ ማውጣት፣ መንግሥት ኃላፊነቱን እንዲወጣ የሚያስገድድ የሕዝብ ድምፅ ሊሆን ይችላል።
የይዘቱ አግባብነትና ሕጋዊነት ጥያቄ ውስጥ የሚወድቅ ቢሆን እንኳ ሊፈታ የሚገባው በሕገ-መንግሥታዊና በሕጋዊ ሥርዓቶች መዋቅር ውስጥ ብቻ ነው።
አንድን ጋዜጠኛ ለ10 ቀናት ያለ ፍርድ ቤት ትዕዛዝ ማሰር ሕገ-መንግሥቱን መጣስ ብቻ ሳይሆን፣ በሀገሪቱ የዲሞክራሲ ምኅዳር ላይ የፍርሃት ጥላ (Chilling Effect) የሚያሳድር ድርጊት ነው።
መንግሥት የሕግ የበላይነትን ለማስከበር መጀመሪያ ራሱ በሕግ መገዛት አለበት። ስለሆነም ጋዜጠኛዋ በአስቸኳይ ፍርድ ቤት ልትቀርብ ወይም ሕገ-መንግሥታዊ መብቷ ተከብሮ በአፋጣኝ ልትፈታ ይገባል።
ሕግን ለመጠበቅ በሚደረግ ጉዞ ውስጥ ሕግን መጣስ፣ ራሱ ሌላ የሕግ መፍረስን የሚወልድ በመሆኑ ሥርዓቱ ሊታረም ይገባዋል።
(በፍቅር ለይኩን)፤
2 months ago
የዓለም ዋንጫ ትዝታዎች...
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 4፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የዘንድሮው የዓለም ዋንጫ ከጅማሮው ከኳስ ውበቱ ይልቅ ከጀርባው ያለው ፖለቲካ አይሎ ከመታየቱ ባለፈ በርካታ ውዝግቦችን እያስተናገደ ይገኛል፡፡
በኢትዮጵያ የስፖርት ጋዜጠኝነት ውስጥ ስማቸው ጎልቶ ከሚነሳና የብዙሃንን ቀልብ መሳብ ከቻሉ ባለሙያዎች መካከል አንዱ ነው ጋዜጠኛ ማርቆስ ኤልያስ።
በተለያዩ ታዋቂ ጋዜጦች የስፖርት ዓምድ ላይ ለበርካታ ዓመታት በመጻፍ የዳበረ ልምድ አካብቷል፡፡ ጋዜጠኛ ማርቆስ በሬዲዮ ሞገድም በሚያቀርባቸው ተወዳጅ ስፖርታዊ ዝግጅቶቹ የብዙዎችን ልብ ማሸነፍ ችሏል።
ማርቆስ በተለያዩ መድረኮች ላይ በሚያቀርባቸው ጥልቅ የስፖርት ትንታኔዎች በአድማጭና ተመልካች ዘንድ እጅግ የተወደደ ነው፡፡ በተለይም ያለፉ ክስተቶችን፣ ስታቲስቲክሶችን እና ታሪኮችን በቅጽበት አስታውሶ የመተንተን ልዩ ብቃቱ መለያው ነው።
መተሃራ አካባቢ ተወልዶ ያደገው ማርቆስ፤ የእግር ኳስ ፍቅር ልቡን የገዛው ገና በልጅነቱ ነበር። በወቅቱ ትልቅ ሕልሙ ጎበዝ የእግር ኳስ ተጫዋች መሆን የነበረ ቢሆንም፣ለትምህርት ቅድሚያ በመስጠቱ የእግር ኳስ ህልሙን ሳያሳካ እንደቀረ ያስታውሳል፡፡
ሆኖም ግን የስፖርት ጋዜጠኛው ማርቆስ መጫወት ባይችልም ኳስን በጥልቅ ከመውደዱ የተነሳ ዛሬም የስፖርቱ ዓለም የዕለት ተዕለት ሕይወቱና የሙያ እንጀራው ሆኖ ቀጥሏል።
ሁልጊዜም ቢሆን "የሀገር ውስጥ ስፖርትን ማሳደግ" የዘወትር ትልቅ ምኞቱና የሥራው ዋና ግብ መሆኑን በኩራት ይናገራል።
ዛሬ በጉጉት የሚጠበቀው የዓለም ዋንጫ ውድድር በይፋ የሚጀመርበት ዕለት በመሆኑም ጋዜጠኛው ስለ ውድድሩ ያለፉ ታሪኮች እና ወቅታዊ ሁኔታዎችን በማስመልከት ሰፊ ትንታኔ ሰጥቷል።
ያለፉትን የዓለም ዋንጫ ታሪኮች ሳያሰለች እና ትውስታዎችን እያጣቀሰ የሚተነትነው ማርቆስ፤ ዛሬ ስለሚጀመረው ታላቅ መድረክ አንኳር ሃሳቦችን አንስቷል፡
የዘንድሮው የዓለም ዋንጫ ከጅማሮው ከኳስ ውበቱ ይልቅ፣ ከጀርባው ያለው ፖለቲካ አይሎ የታየበትና በርካታ ውዝግቦችን እያስተናገደ ነው ይላል፡፡
ጋዜጠኛው ማርቆስ ውድድሩ ከመጀመሩ በፊት የነበሩትን የሀገራት ፍጥጫዎች፣ ዓለም አቀፍ ተፅዕኖዎችና ከሜዳ ውጭ ያሉትን ትኩሳት በዝርዝር በመዳሰስ በርካታ አዳዲስ ሃሳቦችንና እይታዎችን አጋርቶናል።
በቅድስት ዘውዱ
ጋዜጠኛ ማርቆስ ኤልያስ ከፋና ፖድካስት ጋር ያደረገውን ቆይታ ለመከታተል ማስፈንጠሪያውን ይጫኑ፦ https://youtu.be/BA7Rsnkzj...
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 4፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የዘንድሮው የዓለም ዋንጫ ከጅማሮው ከኳስ ውበቱ ይልቅ ከጀርባው ያለው ፖለቲካ አይሎ ከመታየቱ ባለፈ በርካታ ውዝግቦችን እያስተናገደ ይገኛል፡፡
በኢትዮጵያ የስፖርት ጋዜጠኝነት ውስጥ ስማቸው ጎልቶ ከሚነሳና የብዙሃንን ቀልብ መሳብ ከቻሉ ባለሙያዎች መካከል አንዱ ነው ጋዜጠኛ ማርቆስ ኤልያስ።
በተለያዩ ታዋቂ ጋዜጦች የስፖርት ዓምድ ላይ ለበርካታ ዓመታት በመጻፍ የዳበረ ልምድ አካብቷል፡፡ ጋዜጠኛ ማርቆስ በሬዲዮ ሞገድም በሚያቀርባቸው ተወዳጅ ስፖርታዊ ዝግጅቶቹ የብዙዎችን ልብ ማሸነፍ ችሏል።
ማርቆስ በተለያዩ መድረኮች ላይ በሚያቀርባቸው ጥልቅ የስፖርት ትንታኔዎች በአድማጭና ተመልካች ዘንድ እጅግ የተወደደ ነው፡፡ በተለይም ያለፉ ክስተቶችን፣ ስታቲስቲክሶችን እና ታሪኮችን በቅጽበት አስታውሶ የመተንተን ልዩ ብቃቱ መለያው ነው።
መተሃራ አካባቢ ተወልዶ ያደገው ማርቆስ፤ የእግር ኳስ ፍቅር ልቡን የገዛው ገና በልጅነቱ ነበር። በወቅቱ ትልቅ ሕልሙ ጎበዝ የእግር ኳስ ተጫዋች መሆን የነበረ ቢሆንም፣ለትምህርት ቅድሚያ በመስጠቱ የእግር ኳስ ህልሙን ሳያሳካ እንደቀረ ያስታውሳል፡፡
ሆኖም ግን የስፖርት ጋዜጠኛው ማርቆስ መጫወት ባይችልም ኳስን በጥልቅ ከመውደዱ የተነሳ ዛሬም የስፖርቱ ዓለም የዕለት ተዕለት ሕይወቱና የሙያ እንጀራው ሆኖ ቀጥሏል።
ሁልጊዜም ቢሆን "የሀገር ውስጥ ስፖርትን ማሳደግ" የዘወትር ትልቅ ምኞቱና የሥራው ዋና ግብ መሆኑን በኩራት ይናገራል።
ዛሬ በጉጉት የሚጠበቀው የዓለም ዋንጫ ውድድር በይፋ የሚጀመርበት ዕለት በመሆኑም ጋዜጠኛው ስለ ውድድሩ ያለፉ ታሪኮች እና ወቅታዊ ሁኔታዎችን በማስመልከት ሰፊ ትንታኔ ሰጥቷል።
ያለፉትን የዓለም ዋንጫ ታሪኮች ሳያሰለች እና ትውስታዎችን እያጣቀሰ የሚተነትነው ማርቆስ፤ ዛሬ ስለሚጀመረው ታላቅ መድረክ አንኳር ሃሳቦችን አንስቷል፡
የዘንድሮው የዓለም ዋንጫ ከጅማሮው ከኳስ ውበቱ ይልቅ፣ ከጀርባው ያለው ፖለቲካ አይሎ የታየበትና በርካታ ውዝግቦችን እያስተናገደ ነው ይላል፡፡
ጋዜጠኛው ማርቆስ ውድድሩ ከመጀመሩ በፊት የነበሩትን የሀገራት ፍጥጫዎች፣ ዓለም አቀፍ ተፅዕኖዎችና ከሜዳ ውጭ ያሉትን ትኩሳት በዝርዝር በመዳሰስ በርካታ አዳዲስ ሃሳቦችንና እይታዎችን አጋርቶናል።
በቅድስት ዘውዱ
ጋዜጠኛ ማርቆስ ኤልያስ ከፋና ፖድካስት ጋር ያደረገውን ቆይታ ለመከታተል ማስፈንጠሪያውን ይጫኑ፦ https://youtu.be/BA7Rsnkzj...
2 months ago
ምሕረት ደግፍ ትውልድና እድገቷ አዲስ አበባ ፤ በልዩ ስሙ ኮልፌ 18 ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ነው። የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርቷን በሐምሌ 19 የመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤት ፣ ሁለተኛ ደረጃን በየካቲት 23 ት/ቤት ፣ የመሰናዶ ትምህርቷን ደግሞ በአዲስ ከተማ መሰናዶ ተከታትላ ጨርሳለች። ቀጥሎም በኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ በመምህርነት በመመረቅ ትምህርቷን ያጠናቀቀች ሲሆን ፤ በአሁኑ ወቅትም በዚሁ ዩኒቨርሲቲ የእንግሊዘኛ ቋንቋ እና ሥነ-ጽሑፍ የመጀመሪያ ዲግሪ ተማሪ ናት።
የጋዜጠኝነት ሞያን ከከፍታ የትምህርት ሥልጠና እና የማማከር ተቋም ያጠናቀቀች ሲሆን ፤ በፋክት ቼኪንግ እና ሌሎችም ተያያዥ ሥልጠናዎችን ከሌሎች የሃገር ውስጥ እና የውጪ ተቋማት በሰርተፊኬት ማግኘት ችላለች።
ከመደበኛው ትምህርት ባሻገር ሙሉ የልጅነት ሕይወቷ ያለፈው በደብረ ገሊላ አማኑኤል እግዚአብሔር ምስሌነ ሰንበት ትምህርት ቤት ነው። አሁን ላለችበትም መሰረት የጣለችው ሰንበት ትምህርት ቤት በነበረችበት ወቅት ነው። በተለይም በሥነ-ጽሑፍ ረገድ ዝንባሌ ሊኖራት የቻለው ከልጅነት ጀምሮ በሰንበት ት/ቤት እና በመደበኛ ት/ቤት በነበራት ተሳትፎ ነው። እንደ ግጥም ፣ መነባንብ ፣ ድራማ እና ሌሎችም ላይ የበዛ ተሳትፎ ታደርግ ነበር። ይህ ተሳትፎ አሁንም ድረስ ተከትሏት በመምጣት ለፍሬ እንደደረሰ ታምናለች።
በት/ቤት ፣ በወረዳ እና በክፍለ ከተማ ብሎም በከተማ አቀፍ በነበሩ የሥነ-ጸሑፍ ውድድሮች ፣ መድረኮች እና መሰል ዝግጅቶች ላይ በመሳተፍ የተለያዩ ሽልማቶችን እና የምስጋና ወረቀቶችን ማግኘት ችላለች። በመንፈሳዊም በኩል በተመሳሳይ ሁኔታ በነበሯት ተሳትፎዎች በርካታ ሽልማቶችን አግኝታለች። እስከዛሬ ድረስም በተለያዩ የሥነ-ጸሑፍ መድረኮች ሥራዎቿን እያቀረበች ትገኛለች።
ከኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ እንደተመረቀች በአጼ ፋሲል የመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤት ለሁለት ዓመት ያህል በመምህርነት አገልግላለች። በሞያው በቆየችባቸው ጥቂት ዓመታት የተለያዩ የምስጋና እና የደረጃ ሽልማቶችን ማግኘት ችላለች።
ከዚያ በመቀጠል በተዋህዶ ሚዲያ ማዕከል ለአንድ ዓመት ያህል በፕሮግራም አዘጋጅነት የሠራች ሲሆን ፤ የራሷን መንፈሳዊ ፕሮግራሞች እና ሥራዎች በመሥራት ቆይታለች። በአሁኑ ወቅት በሃገሬ ቴሌቪዥን በከፍተኛ ሪፖርተርነት መደብ እየሠራች የምትገኝ ሲሆን ፤ ላለፈው አንድ ዓመት ያህል በዚሁ ጣቢያ የዜና ክፍል ባልደረባ በመሆን ቆይታለች።
ከልጅነት ጀምሮ የተከተላት የሥነ-ጽሑፍ ፍቅር አሁንም ድረስ ተከትሏት የመጣ ሲሆን ፤ የመጀመሪያ የሆነውንና ” የውቦች ንግሥት” ስትል የሰየመችውን መጽሐፏን ለአንባቢያን ለማድረስ ዝግጅቷን አጠናቃለች።
Via: Addis Books
የጋዜጠኝነት ሞያን ከከፍታ የትምህርት ሥልጠና እና የማማከር ተቋም ያጠናቀቀች ሲሆን ፤ በፋክት ቼኪንግ እና ሌሎችም ተያያዥ ሥልጠናዎችን ከሌሎች የሃገር ውስጥ እና የውጪ ተቋማት በሰርተፊኬት ማግኘት ችላለች።
ከመደበኛው ትምህርት ባሻገር ሙሉ የልጅነት ሕይወቷ ያለፈው በደብረ ገሊላ አማኑኤል እግዚአብሔር ምስሌነ ሰንበት ትምህርት ቤት ነው። አሁን ላለችበትም መሰረት የጣለችው ሰንበት ትምህርት ቤት በነበረችበት ወቅት ነው። በተለይም በሥነ-ጽሑፍ ረገድ ዝንባሌ ሊኖራት የቻለው ከልጅነት ጀምሮ በሰንበት ት/ቤት እና በመደበኛ ት/ቤት በነበራት ተሳትፎ ነው። እንደ ግጥም ፣ መነባንብ ፣ ድራማ እና ሌሎችም ላይ የበዛ ተሳትፎ ታደርግ ነበር። ይህ ተሳትፎ አሁንም ድረስ ተከትሏት በመምጣት ለፍሬ እንደደረሰ ታምናለች።
በት/ቤት ፣ በወረዳ እና በክፍለ ከተማ ብሎም በከተማ አቀፍ በነበሩ የሥነ-ጸሑፍ ውድድሮች ፣ መድረኮች እና መሰል ዝግጅቶች ላይ በመሳተፍ የተለያዩ ሽልማቶችን እና የምስጋና ወረቀቶችን ማግኘት ችላለች። በመንፈሳዊም በኩል በተመሳሳይ ሁኔታ በነበሯት ተሳትፎዎች በርካታ ሽልማቶችን አግኝታለች። እስከዛሬ ድረስም በተለያዩ የሥነ-ጸሑፍ መድረኮች ሥራዎቿን እያቀረበች ትገኛለች።
ከኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ እንደተመረቀች በአጼ ፋሲል የመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤት ለሁለት ዓመት ያህል በመምህርነት አገልግላለች። በሞያው በቆየችባቸው ጥቂት ዓመታት የተለያዩ የምስጋና እና የደረጃ ሽልማቶችን ማግኘት ችላለች።
ከዚያ በመቀጠል በተዋህዶ ሚዲያ ማዕከል ለአንድ ዓመት ያህል በፕሮግራም አዘጋጅነት የሠራች ሲሆን ፤ የራሷን መንፈሳዊ ፕሮግራሞች እና ሥራዎች በመሥራት ቆይታለች። በአሁኑ ወቅት በሃገሬ ቴሌቪዥን በከፍተኛ ሪፖርተርነት መደብ እየሠራች የምትገኝ ሲሆን ፤ ላለፈው አንድ ዓመት ያህል በዚሁ ጣቢያ የዜና ክፍል ባልደረባ በመሆን ቆይታለች።
ከልጅነት ጀምሮ የተከተላት የሥነ-ጽሑፍ ፍቅር አሁንም ድረስ ተከትሏት የመጣ ሲሆን ፤ የመጀመሪያ የሆነውንና ” የውቦች ንግሥት” ስትል የሰየመችውን መጽሐፏን ለአንባቢያን ለማድረስ ዝግጅቷን አጠናቃለች።
Via: Addis Books
2 months ago
የዓለም የፕሬስ ነፃነት ታይቶ
በማይታወቅ ሁኔታ አሽቆልቁሏል
የድንበር የለሽ ጋዜጠኞች ድርጅት (RSF) ባወጣው የ25ኛ ዓመት ዓለም አቀፍ መግለጫ መሠረት፣ በዓለም ዙሪያ የሚዲያ ነፃነት ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ ማሽቆልቆሉንና ጋዜጠኝነትን ወደ ወንጀል የመቀየር ሂደት መባባሱን አስታውቋል።
በአሁኑ ወቅት አምባገነን መንግሥታት የሚዲያ ነፃነትን ለማፈን የብሔራዊ ደኅንነት ሕግጋትን እንደ መሣሪያ እየተጠቀሙበት እንደሚገኙ ድርጅቱ የገለጸ ሲሆን፣ ኖርዌይ ለ10ኛ ተከታታይ ዓመት 1ኛ ደረጃን በመያዝ የዓለም የፕሬስ ነጻነትን በማስፈን ግንባር ቀደምነቷን አስመስክራለች። በአንጻሩ አሜሪካ በሚዲያ ላይ በሚሰነዘሩ የፖለቲካ ጥቃቶች ምክንያት በ7 ደረጃዎች በማሽቆልቆል 64ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጣለች።
በዚሁ ዓለም አቀፍ የደረጃ ሰንጠረዥ መሠረት ኢትዮጵያ ከ180 የዓለም ሀገራት መካከል 148ኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች፤ ለዚህም በሀገሪቱ አራት ጋዜጠኞች ከፀረ-ሽብርተኝነት ሕግ ጋር በተያያዘ ክስ ለሦስት ዓመታት ታስረው መቆየታቸው በሕጋዊ መመዘኛ ዝቅተኛ ውጤት እንድታገኝ ማድረጉ ተገልጿል። ከአፍሪካ ቀንድ ሀገራት መካከል የእርስ በርስ ጦርነት ውስጥ የምትገኘው ሱዳን 161ኛ ደረጃን ስትይዝ፣ ኤርትራ ደግሞ 180ኛ በመሆን ከዓለም የመጨረሻውን ደረጃ ይዛለች።
Seledadotio
Seledadotio
በማይታወቅ ሁኔታ አሽቆልቁሏል
የድንበር የለሽ ጋዜጠኞች ድርጅት (RSF) ባወጣው የ25ኛ ዓመት ዓለም አቀፍ መግለጫ መሠረት፣ በዓለም ዙሪያ የሚዲያ ነፃነት ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ ማሽቆልቆሉንና ጋዜጠኝነትን ወደ ወንጀል የመቀየር ሂደት መባባሱን አስታውቋል።
በአሁኑ ወቅት አምባገነን መንግሥታት የሚዲያ ነፃነትን ለማፈን የብሔራዊ ደኅንነት ሕግጋትን እንደ መሣሪያ እየተጠቀሙበት እንደሚገኙ ድርጅቱ የገለጸ ሲሆን፣ ኖርዌይ ለ10ኛ ተከታታይ ዓመት 1ኛ ደረጃን በመያዝ የዓለም የፕሬስ ነጻነትን በማስፈን ግንባር ቀደምነቷን አስመስክራለች። በአንጻሩ አሜሪካ በሚዲያ ላይ በሚሰነዘሩ የፖለቲካ ጥቃቶች ምክንያት በ7 ደረጃዎች በማሽቆልቆል 64ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጣለች።
በዚሁ ዓለም አቀፍ የደረጃ ሰንጠረዥ መሠረት ኢትዮጵያ ከ180 የዓለም ሀገራት መካከል 148ኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች፤ ለዚህም በሀገሪቱ አራት ጋዜጠኞች ከፀረ-ሽብርተኝነት ሕግ ጋር በተያያዘ ክስ ለሦስት ዓመታት ታስረው መቆየታቸው በሕጋዊ መመዘኛ ዝቅተኛ ውጤት እንድታገኝ ማድረጉ ተገልጿል። ከአፍሪካ ቀንድ ሀገራት መካከል የእርስ በርስ ጦርነት ውስጥ የምትገኘው ሱዳን 161ኛ ደረጃን ስትይዝ፣ ኤርትራ ደግሞ 180ኛ በመሆን ከዓለም የመጨረሻውን ደረጃ ይዛለች።
Seledadotio
Seledadotio
Sponsored by
Surafel
2 months ago
💍 ጋዜጠኛ አዳነ አረጋ እና ባለቤቱ ቢታንያ በሰይፉ_ሾው ያደረጉት አስገራሚ ቆይታ እና ያልተሰሙ እውነታዎች! 💕
#ethiopia | ታዋቂው ጋዜጠኛ አዳነ አረጋ እና ውብ ባለቤቱ ቢታንያ በሰይፉ ሾው ቀርበው ስለ ፍቅራቸው፣ ስለ ትዳራቸው እና ስለ ህይወታቸው ጣፋጭና አስቂኝ ገጠመኞችን አካፍለዋል። ከቆይታቸው የተወሰዱ ድንቅ ነጥቦች እነሆ፦
🎙 ጋዜጠኛ አዳነ አረጋ...
* ⚽️ "የሰርጌ ቀን አርሰናል ዋንጫ ካልበላ አላገባም ብዬ ነበር!"
* 📺 "ሚዲያ ላይ ስለማታውቀኝ ነው የጠቀመኝ፤ ለእኔ እሷን ለማጥናት 6 ወር በቂ ነበር። ከውበቷ ውጪ አስተሳሰቧ 'ውይ' የሚያስብል ነው፤ በትውውቅ 4 ዓመት ሆኖናል።"
* 🎬 "ማስታወቂያ እንድትሰራ እኔ ነኝ በግድ ያስገባኋት፤ ፈጣሪ የሰጣትን ቁንጅና እና አቋም መጠቀም አለባት።"
* 👩ያ "እናትዬ ብዬ ነው የምጠራት።"
* 💼 "በጋዜጠኝነት ደመወዝ ብቻ ልትኖር አትችልም። ስራ እወዳለሁ፤ የተለያዩ ኢቨንቶችን እሰራለሁ።"
* 🍲 "የማይሰለቸኝ ምግብ ሽሮ ነው።"
* 📺 "ቀጥታ ስርጭት ዜና እያነበብኩኝ ወንበሩ ሰምጦብኝ ያውቃል! ካሜራ ማናችንም ከነካሜራው ከአውሮፕላን ላይ ወድቆብናል።"
* 🎶 "የሀገር ካስማ ከተሰኘው ዘፈን ፕሮዲውሰሮች አንዱ ነበርኩኝ። የቴዲ ታደሰን 'በቸር ይደር' እና የጥላሁንን 'አምሳሉ' ዘፈኖችን እወዳለሁ።"
* ⛰ "ጊሸን ሄጄ እንደመጣሁ ነው ፀሎቴ የሰመረልኝ። መስከረም 21 እኔም እናቴም የተወለድንበት ቀን ነው።"
* 🎤 "የሰርጌ ቀን ድምፃዊ ጎሳዬ፣ አብነት እና ዳዊት ይኖራሉ።"
👸 ባለቤቱ ቢታንያ ...
* 🏪 "እኔ ሱቅ እቃ ሊገዛ መጥቶ ነው የተዋወቅነው። ሰዎች እስኪነግሩኝ ድረስ ጋዜጠኛ መሆኑን አላውቅም ነበር።"
* 💍 "የ'ታገቢኛለሽ' ሰርፕራይዙ በጣም ደስ ይል ነበር።"
* 🐕 "አዳነ ውሻ አምጥቶልኝ ሰርፕራይዝ አድርጎኛል። 'አባትዬ' ብዬ ነው የምጠራው።"
* 👩❤️👨 "አዳነ ፍቅር መስጠት ይችላል፤ የተካነበት ነው። ልክ እንደ አባቴ አይነት ባል ነው ያገኘሁት።"
* 💭 "ሰዎች ተጋብተው ከሚጣሉ ይልቅ መጀመሪያ ተጣልተው ነው መጋባት ያለባቸው።"
* 🥩 "ጥሬ ስጋ እና ጭኮ እወዳለሁ፤ የንዋይ ደበበን 'አሜን' ዘፈን እመርጣለሁ።"
* 📱 "የእድል ቁጥሬ 6 ስለሆነ 6 ልጆች ቢኖሩኝ ደስ ይለኛል!
የአዴ እና የቢቱ ፍቅር ፍጻሜው ለሰርግ በቃ! አዴ አንተ ሰው አክባሪና ትሁት ጋዜጠኛ እንኳን ደስ አለህ። ለሁለታችሁም ዘላቂና ደስተኛ የትዳር ዘመን እንመኛለን! 🥂🎉
Via Zerihun Teznanu
#ethiopia | ታዋቂው ጋዜጠኛ አዳነ አረጋ እና ውብ ባለቤቱ ቢታንያ በሰይፉ ሾው ቀርበው ስለ ፍቅራቸው፣ ስለ ትዳራቸው እና ስለ ህይወታቸው ጣፋጭና አስቂኝ ገጠመኞችን አካፍለዋል። ከቆይታቸው የተወሰዱ ድንቅ ነጥቦች እነሆ፦
🎙 ጋዜጠኛ አዳነ አረጋ...
* ⚽️ "የሰርጌ ቀን አርሰናል ዋንጫ ካልበላ አላገባም ብዬ ነበር!"
* 📺 "ሚዲያ ላይ ስለማታውቀኝ ነው የጠቀመኝ፤ ለእኔ እሷን ለማጥናት 6 ወር በቂ ነበር። ከውበቷ ውጪ አስተሳሰቧ 'ውይ' የሚያስብል ነው፤ በትውውቅ 4 ዓመት ሆኖናል።"
* 🎬 "ማስታወቂያ እንድትሰራ እኔ ነኝ በግድ ያስገባኋት፤ ፈጣሪ የሰጣትን ቁንጅና እና አቋም መጠቀም አለባት።"
* 👩ያ "እናትዬ ብዬ ነው የምጠራት።"
* 💼 "በጋዜጠኝነት ደመወዝ ብቻ ልትኖር አትችልም። ስራ እወዳለሁ፤ የተለያዩ ኢቨንቶችን እሰራለሁ።"
* 🍲 "የማይሰለቸኝ ምግብ ሽሮ ነው።"
* 📺 "ቀጥታ ስርጭት ዜና እያነበብኩኝ ወንበሩ ሰምጦብኝ ያውቃል! ካሜራ ማናችንም ከነካሜራው ከአውሮፕላን ላይ ወድቆብናል።"
* 🎶 "የሀገር ካስማ ከተሰኘው ዘፈን ፕሮዲውሰሮች አንዱ ነበርኩኝ። የቴዲ ታደሰን 'በቸር ይደር' እና የጥላሁንን 'አምሳሉ' ዘፈኖችን እወዳለሁ።"
* ⛰ "ጊሸን ሄጄ እንደመጣሁ ነው ፀሎቴ የሰመረልኝ። መስከረም 21 እኔም እናቴም የተወለድንበት ቀን ነው።"
* 🎤 "የሰርጌ ቀን ድምፃዊ ጎሳዬ፣ አብነት እና ዳዊት ይኖራሉ።"
👸 ባለቤቱ ቢታንያ ...
* 🏪 "እኔ ሱቅ እቃ ሊገዛ መጥቶ ነው የተዋወቅነው። ሰዎች እስኪነግሩኝ ድረስ ጋዜጠኛ መሆኑን አላውቅም ነበር።"
* 💍 "የ'ታገቢኛለሽ' ሰርፕራይዙ በጣም ደስ ይል ነበር።"
* 🐕 "አዳነ ውሻ አምጥቶልኝ ሰርፕራይዝ አድርጎኛል። 'አባትዬ' ብዬ ነው የምጠራው።"
* 👩❤️👨 "አዳነ ፍቅር መስጠት ይችላል፤ የተካነበት ነው። ልክ እንደ አባቴ አይነት ባል ነው ያገኘሁት።"
* 💭 "ሰዎች ተጋብተው ከሚጣሉ ይልቅ መጀመሪያ ተጣልተው ነው መጋባት ያለባቸው።"
* 🥩 "ጥሬ ስጋ እና ጭኮ እወዳለሁ፤ የንዋይ ደበበን 'አሜን' ዘፈን እመርጣለሁ።"
* 📱 "የእድል ቁጥሬ 6 ስለሆነ 6 ልጆች ቢኖሩኝ ደስ ይለኛል!
የአዴ እና የቢቱ ፍቅር ፍጻሜው ለሰርግ በቃ! አዴ አንተ ሰው አክባሪና ትሁት ጋዜጠኛ እንኳን ደስ አለህ። ለሁለታችሁም ዘላቂና ደስተኛ የትዳር ዘመን እንመኛለን! 🥂🎉
Via Zerihun Teznanu
3 months ago
አፍሪካ ተቀይራለች በጣም ያማረና አስደናቂ ቦታ ነው‼️
ዲላን ፔጅ የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩትን ጎበኘ
አዲስ አበባ — በዓለማቀፍ ደረጃ በሚሊዮኖች ዘንድ ተወዳጅነትን ያተረፈው ታዋቂው የዲጂታል ጋዜጠኛ እና የማህበራዊ ሚዲያ ይዘት ፈጣሪ ዲላን ፔጅ (Dylan Page) በኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት የስራ ጉብኝት አደረገ።
ጉብኝቱ በተቋሙ ውስጥ እየተከናወኑ ያሉ የቴክኖሎጂ ፈጠራዎችን እና የምርምር ስራዎችን በቅርብ ለመመልከት ያለመ መሆኑ ታውቋል።
ዲላን ፔጅ በኢንስቲትዩቱ ባደረገው ቆይታ የተመለከታቸውን ዘመናዊ የቴክኖሎጂ ስራዎች አድንቆ፣ ጉብኝቱ ስለ አፍሪካ አህጉር ያለውን የተሳሳተ ግንዛቤ የሚቀይር መሆኑን ገልጿል። ይዘት ፈጣሪው በሰጠው አስተያየት፡
"ይህን በቴክኖሎጂ የተቃኘ ቦታ ሳየው እጅግ ተደምሜያለሁ፤ በጣም ያማረና አስደናቂ ቦታ ነው። አፍሪካ ተቀይራለች፤ ይህ ተቋም ደግሞ የአህጉሪቱን አዲስ ገፅታ ለዓለም የሚያሳይ ስፍራ ሆኖ አግኝቼዋለሁ። ባየሁት ነገር ሁሉ እጅግ ደስተኛ ነኝ።"
ዲላን ፔጅ እና በዲጂታል ጋዜጠኝነት ያለው ተፅዕኖ
በፈጣን፣ አጭር፣ ሳቢ እና ለመረዳት ቀላል በሆኑ አቀራረቦች ዓለማቀፍ ዜናዎችን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለወጣቱ ትውልድ በማድረስ የሚታወቀው ዲላን ፔጅ፣ በማህበራዊ ሚዲያ ላይ ከፍተኛ ተፅዕኖ ካላቸው ግለሰቦች መካከል አንዱ ነው።
በተለይም በቲክቶክ (TikTok) ገጹ ከ19 ሚሊዮን በላይ ተከታዮችን ማፍራት የቻለው ዲላን፣ ወጣቱ ትውልድ መረጃና ዜናዎችን የሚቀበልበትን ባህላዊ መንገድ በመቀየር ረገድ በዓለም አቀፍ ደረጃ ግንባር ቀደም ተጠቃሽ መሆን ችሏል።
Via የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት
seledadotio
seledadotio
ዲላን ፔጅ የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩትን ጎበኘ
አዲስ አበባ — በዓለማቀፍ ደረጃ በሚሊዮኖች ዘንድ ተወዳጅነትን ያተረፈው ታዋቂው የዲጂታል ጋዜጠኛ እና የማህበራዊ ሚዲያ ይዘት ፈጣሪ ዲላን ፔጅ (Dylan Page) በኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት የስራ ጉብኝት አደረገ።
ጉብኝቱ በተቋሙ ውስጥ እየተከናወኑ ያሉ የቴክኖሎጂ ፈጠራዎችን እና የምርምር ስራዎችን በቅርብ ለመመልከት ያለመ መሆኑ ታውቋል።
ዲላን ፔጅ በኢንስቲትዩቱ ባደረገው ቆይታ የተመለከታቸውን ዘመናዊ የቴክኖሎጂ ስራዎች አድንቆ፣ ጉብኝቱ ስለ አፍሪካ አህጉር ያለውን የተሳሳተ ግንዛቤ የሚቀይር መሆኑን ገልጿል። ይዘት ፈጣሪው በሰጠው አስተያየት፡
"ይህን በቴክኖሎጂ የተቃኘ ቦታ ሳየው እጅግ ተደምሜያለሁ፤ በጣም ያማረና አስደናቂ ቦታ ነው። አፍሪካ ተቀይራለች፤ ይህ ተቋም ደግሞ የአህጉሪቱን አዲስ ገፅታ ለዓለም የሚያሳይ ስፍራ ሆኖ አግኝቼዋለሁ። ባየሁት ነገር ሁሉ እጅግ ደስተኛ ነኝ።"
ዲላን ፔጅ እና በዲጂታል ጋዜጠኝነት ያለው ተፅዕኖ
በፈጣን፣ አጭር፣ ሳቢ እና ለመረዳት ቀላል በሆኑ አቀራረቦች ዓለማቀፍ ዜናዎችን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለወጣቱ ትውልድ በማድረስ የሚታወቀው ዲላን ፔጅ፣ በማህበራዊ ሚዲያ ላይ ከፍተኛ ተፅዕኖ ካላቸው ግለሰቦች መካከል አንዱ ነው።
በተለይም በቲክቶክ (TikTok) ገጹ ከ19 ሚሊዮን በላይ ተከታዮችን ማፍራት የቻለው ዲላን፣ ወጣቱ ትውልድ መረጃና ዜናዎችን የሚቀበልበትን ባህላዊ መንገድ በመቀየር ረገድ በዓለም አቀፍ ደረጃ ግንባር ቀደም ተጠቃሽ መሆን ችሏል።
Via የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት
seledadotio
seledadotio
3 months ago
የስመኝ ግዛውን መፅሐፍ ይግዙ!!!!!
*48 ሰዓት ሳይሞላ 1000 የመፅሀፍ ኮፒ በቅድመ ሽያጭ ተሸጠ
#ethiopia | ቅዳሜ ግንቦት 8 2018 ምሽት ላይ የተጀመረው "የእናቴ ሮሚዬ" የቅድመ ግዢ ቻሌንጅ ተጠናክሯል። 1000 መፅሀፎች በመሸጣቸው ደራሲዋ ስመኝ ግዛው የከበረ ምስጋናዋን አቅርባለች።
ከደራሲዋ ጎን ቆሞ ቻሌንጁን ያስጀመራት ተወዳጅ ሚድያም የማስተዋወቁን እና መፅሀፉን ግዟት በሚል የጀመረውን ቅስቀሳ አጠናክሮ ይቀጥላል ።
ተወዳጅ ሚድያ ስመኝን ለሚያውቁ ሁሉ መረጃውን በቴሌግራም ፣ በሜሴንጀር እና በሌሎችም መንገዶች እያደረሰ ሲሆን መፅሀፍ የገዙ ሰዎችን ከእነ ስማቸው እና አጭር ታሪካቸው ማውጣታችን ይከተላል። ድር ቢያብር አንበሳ ያስር እንዲሉ ነገ እርስዎም መፅሀፍ ቢያሳትሙ አጠገብዎ ሰው ያስፈልጋልና ነገ ሳይሉ ዛሬ በቻሌንጁ ይሳተፉ።
የቅድመ-መጽሐፍ ግዢ (Pre-Order) እና የአጋርነት ጥሪ!
ላለፉት ሁለት አስርተ ዓመታት በጋዜጠኝነት እና በድንቅ የፈጠራ ሥራዎቿ የምናውቃት ደራሲ ስመኝ ግዛው፣ «የእናቴ ሮሚዮ» የተሰኘውን አዲስ የአጫጭር ልቦለዶች መድብል ለንባብ ልታበቃ ጥቂት ቀናት ቀርተዋታል።
በመሆኑም፣ የስነ-ጽሑፍ አፍቃሪያን፣ የደራሲዋ ሥራዎች አድናቂዎች፣ ተቋማትና ወዳጆች መጽሐፉን በቅድመ-ግዢ ፓኬጆች በመግዛት አጋርነታችሁን እንድታሳዩ በአክብሮት ተጋብዛችኋል።
የቅድመ-ግዢ ፓኬጆች እና የዋጋ ዝርዝር፦
• 5 መጽሐፍ፦ 2,500 ብር
• 10 መጽሐፍት፦ 5,000 ብር
• 20 መጽሐፍት፦ 10,000 ብር
• 30 መጽሐፍት፦ 15,000 ብር
• 40 መጽሐፍት፦ 20,000 ብር
• 50 መጽሐፍት፦ 25,000 ብር
💳 የክፍያ እና የምዝገባ መመሪያ፦
1. ክፍያውን በሚከተለው የባንክ አካውንት ያስገቡ፦
o የባንክ አካውንት ቁጥር ፦ ኢት. ንግድ ባንክ 1000345019158
o ቴሌ ብር፦ ____0966925299
o የአካውንት ስም፦ ስመኝ ግዛው
2. ክፍያውን ከፈጸሙ በኋላ፣ የማረጋገጫ ደረሰኙን (Screenshot) በቴሌግራም አድራሻችን ይላኩ፦
የቴሌግራም ሊንክ/ዩዘርኔም፦ https://t.me/SimegnGizaw
• አስፈላጊ ማሳሰቢያ፦ መጽሐፉን በቅድመ-ግዢ በመግዛት ለምታሳዩት ድጋፍና ውድ አጋርነት ልዩ እውቅና ለመስጠት ስለምንፈልግ፤ ከክፍያ ደረሰኙ ጋር ስለራስዎ የሚገልጽ አጭር መግለጫ (Bio) እና ፎቶግራፍዎን አያይዘው እንዲልኩልን በአክብሮት እንመክራለን።
ስለ ቅን አጋርነታችሁ አስቀድመን እናመሰግናለን!
*48 ሰዓት ሳይሞላ 1000 የመፅሀፍ ኮፒ በቅድመ ሽያጭ ተሸጠ
#ethiopia | ቅዳሜ ግንቦት 8 2018 ምሽት ላይ የተጀመረው "የእናቴ ሮሚዬ" የቅድመ ግዢ ቻሌንጅ ተጠናክሯል። 1000 መፅሀፎች በመሸጣቸው ደራሲዋ ስመኝ ግዛው የከበረ ምስጋናዋን አቅርባለች።
ከደራሲዋ ጎን ቆሞ ቻሌንጁን ያስጀመራት ተወዳጅ ሚድያም የማስተዋወቁን እና መፅሀፉን ግዟት በሚል የጀመረውን ቅስቀሳ አጠናክሮ ይቀጥላል ።
ተወዳጅ ሚድያ ስመኝን ለሚያውቁ ሁሉ መረጃውን በቴሌግራም ፣ በሜሴንጀር እና በሌሎችም መንገዶች እያደረሰ ሲሆን መፅሀፍ የገዙ ሰዎችን ከእነ ስማቸው እና አጭር ታሪካቸው ማውጣታችን ይከተላል። ድር ቢያብር አንበሳ ያስር እንዲሉ ነገ እርስዎም መፅሀፍ ቢያሳትሙ አጠገብዎ ሰው ያስፈልጋልና ነገ ሳይሉ ዛሬ በቻሌንጁ ይሳተፉ።
የቅድመ-መጽሐፍ ግዢ (Pre-Order) እና የአጋርነት ጥሪ!
ላለፉት ሁለት አስርተ ዓመታት በጋዜጠኝነት እና በድንቅ የፈጠራ ሥራዎቿ የምናውቃት ደራሲ ስመኝ ግዛው፣ «የእናቴ ሮሚዮ» የተሰኘውን አዲስ የአጫጭር ልቦለዶች መድብል ለንባብ ልታበቃ ጥቂት ቀናት ቀርተዋታል።
በመሆኑም፣ የስነ-ጽሑፍ አፍቃሪያን፣ የደራሲዋ ሥራዎች አድናቂዎች፣ ተቋማትና ወዳጆች መጽሐፉን በቅድመ-ግዢ ፓኬጆች በመግዛት አጋርነታችሁን እንድታሳዩ በአክብሮት ተጋብዛችኋል።
የቅድመ-ግዢ ፓኬጆች እና የዋጋ ዝርዝር፦
• 5 መጽሐፍ፦ 2,500 ብር
• 10 መጽሐፍት፦ 5,000 ብር
• 20 መጽሐፍት፦ 10,000 ብር
• 30 መጽሐፍት፦ 15,000 ብር
• 40 መጽሐፍት፦ 20,000 ብር
• 50 መጽሐፍት፦ 25,000 ብር
💳 የክፍያ እና የምዝገባ መመሪያ፦
1. ክፍያውን በሚከተለው የባንክ አካውንት ያስገቡ፦
o የባንክ አካውንት ቁጥር ፦ ኢት. ንግድ ባንክ 1000345019158
o ቴሌ ብር፦ ____0966925299
o የአካውንት ስም፦ ስመኝ ግዛው
2. ክፍያውን ከፈጸሙ በኋላ፣ የማረጋገጫ ደረሰኙን (Screenshot) በቴሌግራም አድራሻችን ይላኩ፦
የቴሌግራም ሊንክ/ዩዘርኔም፦ https://t.me/SimegnGizaw
• አስፈላጊ ማሳሰቢያ፦ መጽሐፉን በቅድመ-ግዢ በመግዛት ለምታሳዩት ድጋፍና ውድ አጋርነት ልዩ እውቅና ለመስጠት ስለምንፈልግ፤ ከክፍያ ደረሰኙ ጋር ስለራስዎ የሚገልጽ አጭር መግለጫ (Bio) እና ፎቶግራፍዎን አያይዘው እንዲልኩልን በአክብሮት እንመክራለን።
ስለ ቅን አጋርነታችሁ አስቀድመን እናመሰግናለን!
3 months ago
ፋና የስልጠና ማዕከል እውቅና ባገኘባቸው የቪዲዮግራፊና ፎቶግራፊ፣ ኤዲቲንግ፣ ግራፊክስ ዲዛይን፣ በጋዜጠኝነትና በሚዲያ ቴክኖሎጂ የሙያ መስኮች ስልጠና እየሰጠ ይገኛል።
እርስዎ በእነዚህ የሙያ መስኮች ጎበዝ ባለሙያ መሆን ይሻሉ?
እንግዲያውስ ይፍጠኑ! የካበተ ልምድና እውቀታችንን ይጋሩ!
Sponsored by
Surafel
Comments