10 days ago
ዓይኖቹን ወደ ማስታወቂያ ሰሌዳነት የለወጠው ጉደኛ አትሌት
#ethiopia | በ1996ቱ የአትላንታ ኦሊምፒክ ወቅት አዘጋጆቹ የፑማ ኩባንያን የንግድ ምልክት ከስፖርት መድረኩ ለማራቅ ጥረት አድርገው ነበር።
ነገር ግን እንግሊዛዊው የሩጫ ሻምፒዮን ሊንፎርድ ክሪስቲ የኦሊምፒክ ባለስልጣናትን ያስደነገጠ ሌላ ዕቅድ ይዞ ቀረበ። የወንዶች የ100 ሜትር ውድድር ከመጀመሩ አንድ ቀን ቀደም ብሎ ክሪስቲ ጥቁር መነፅር አድርጎ የጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ተገኘ።
አትሌቱ ጥቁር መነፅሩን ሲያወልቅ በቦታው የነበሩ ጋዜጠኞችና ፎቶግራፈሮች ያልተጠበቀ ነገር ገጠማቸው።
ከዓይኖቹ ላይ ያደረጋቸው ደማቅ ሰማያዊ ኮንታክት ሌንሶች የፑማን ታዋቂ የዘላይ ድመት አርማ ይዘው ነበር። የፎቶግራፈሮች ካሜራዎች ምስሉን ወዲያውኑ የቀረፁ ሲሆን የክሪስቲ የንግድ አርማ ያረፈባቸው ዓይኖች ምስል በዓለም ዙሪያ በፍጥነት ተሰራጩት።
ምንም እንኳን የኦሊምፒክ ባለስልጣናት አትሌቱ በውድድሩ ወቅት ሌንሶቹን እንዳያደርግ በኋላ ላይ ቢከለክሉም ኩባንያው የሚፈልገውን ዓላማ አስቀድሞ አሳካ።
ክሪስቲም ቢልቦርድ፣ የቴሌቪዥን ማስታወቂያ ወይም በትራክ ልብሱ ላይ የሰፈረ አርማ ሳይያስፈልገው የራሱን ዓይኖች ወደ ማስታወቂያ ሰሌዳነት በመለወጥ በስፖርቱ ታሪክ ከታዩት ድብቅ ማስታወቂያ ስልቶች አንዱን ፈጽሟል።
በያፌት ገ/ህይወት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#ethiopia | በ1996ቱ የአትላንታ ኦሊምፒክ ወቅት አዘጋጆቹ የፑማ ኩባንያን የንግድ ምልክት ከስፖርት መድረኩ ለማራቅ ጥረት አድርገው ነበር።
ነገር ግን እንግሊዛዊው የሩጫ ሻምፒዮን ሊንፎርድ ክሪስቲ የኦሊምፒክ ባለስልጣናትን ያስደነገጠ ሌላ ዕቅድ ይዞ ቀረበ። የወንዶች የ100 ሜትር ውድድር ከመጀመሩ አንድ ቀን ቀደም ብሎ ክሪስቲ ጥቁር መነፅር አድርጎ የጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ተገኘ።
አትሌቱ ጥቁር መነፅሩን ሲያወልቅ በቦታው የነበሩ ጋዜጠኞችና ፎቶግራፈሮች ያልተጠበቀ ነገር ገጠማቸው።
ከዓይኖቹ ላይ ያደረጋቸው ደማቅ ሰማያዊ ኮንታክት ሌንሶች የፑማን ታዋቂ የዘላይ ድመት አርማ ይዘው ነበር። የፎቶግራፈሮች ካሜራዎች ምስሉን ወዲያውኑ የቀረፁ ሲሆን የክሪስቲ የንግድ አርማ ያረፈባቸው ዓይኖች ምስል በዓለም ዙሪያ በፍጥነት ተሰራጩት።
ምንም እንኳን የኦሊምፒክ ባለስልጣናት አትሌቱ በውድድሩ ወቅት ሌንሶቹን እንዳያደርግ በኋላ ላይ ቢከለክሉም ኩባንያው የሚፈልገውን ዓላማ አስቀድሞ አሳካ።
ክሪስቲም ቢልቦርድ፣ የቴሌቪዥን ማስታወቂያ ወይም በትራክ ልብሱ ላይ የሰፈረ አርማ ሳይያስፈልገው የራሱን ዓይኖች ወደ ማስታወቂያ ሰሌዳነት በመለወጥ በስፖርቱ ታሪክ ከታዩት ድብቅ ማስታወቂያ ስልቶች አንዱን ፈጽሟል።
በያፌት ገ/ህይወት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
24 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) ትንሿን የባህረ ሰላጤዋን ሀገር በዓለማችን ላይ እጅግ ባለጸጋ እና ከፍተኛ ተጽዕኖ ፈጣሪ ወደ ሆነች ግዙፍ ሀገርነት የቀየሩት የቀድሞው የኳታር አሚር ሼክ ሐማድ ቢን ኻሊፋ አል ታኒ በ74 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል። ማራኪ ስብዕና እና ወዳጃዊ አቀራረብ የነበራቸው እኚህ "አባት አሚር"... የዘመናዊቷ ኳታር እውነተኛ አርክቴክት ተብለው በሰፊው ይወደሳሉ።
እ.ኤ.አ በጥር 1952 በዶሃ የተወለዱት ሼክ ሐማድ፣ ከብሪታንያው ሮያል ሚሊተሪ አካዳሚ ከተመረቁ በኋላ የኳታር የጦር ኃይሎች አዛዥ በመሆን አገልግለዋል። በ1977 አልጋ ወራሽ እና የመከላከያ ሚኒስትር ሆነው የተሾሙ ሲሆን፣ በሰኔ 27፣ 1995 ደግሞ የሀገሪቱን የስልጣን መንበር በይፋ ተረከቡ። ወደ ስልጣን ከመጡበት ጊዜ አንስቶ ሀገራቸው ያላትን እጅግ ሰፊ የተፈጥሮ ጋዝ ሀብት በመጠቀም ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ ማሻሻያዎችን ያካተተ ትልቅ የልማት ራዕይ ነድፈው በተግባር አሳይተዋል።
በሳቸው የስልጣን ዘመን የኳታር አጠቃላይ የሀገር ውስጥ ምርት (GDP) ከ24 እጥፍ በላይ በሚያስገርም ፍጥነት አድጓል። በተለይም ከኖርዝ ፊልድ የተገኘው ምርት፣ ኳታርን እ.ኤ.አ በ2006 የዓለማችን ትልቋ የፈሳሽ የተፈጥሮ ጋዝ (LNG) ላኪ ሀገር እንድትሆን አድርጓታል። በመንግስት መረጃ መሰረት... ይህች ትንሽ ሀገር በአጭር ጊዜ ውስጥ የማምረት አቅሟን በዓመት ወደ 77 ሚሊዮን ቶን ማድረስ ችላ ነበር።
የሼክ ሐማድ የአመራር ዘመን በለውጥ የተሞላ ነበር። የኳታር ፋውንዴሽን መመስረት፣ በ1996 የዓለምን የሚዲያ ትኩረት የሳበው የአልጀዚራ የዜና ቻናል መከፈት፣ በ2004 የመጀመሪያው ቋሚ የኳታር ህገ-መንግስት መጽደቅ እና ሴቶች የመምረጥና የመመረጥ መብት ያገኙበት የማዘጋጃ ቤት ምርጫ መጀመር የሳቸው ትሩፋቶች ናቸው። ከዚህም በላይ ኳታር በ2022ቱን የፊፋ ዓለም ዋንጫ የማስተናገድ መብት እንድታገኝ ያደረጉት ጥረት፣ አንዲት አረብ ሀገር ይህንን ታላቅ ውድድር ስታስተናግድ በታሪክ የመጀመሪያው እንዲሆን አስችሏል።
ሼክ ሐማድ ኳታርን የዓለም አቀፍ ዲፕሎማሲ ማዕከል እና የሰላም አደራዳሪ እንድትሆን ሰፊ ራዕይ ነበራቸው። በሱዳን ዳርፉር ክልል፣ በሊባኖስ የውስጥ ትርምስ፣ እንዲሁም በፍልስጤሙ ሃማስ እና ፋታህ መካከል ለተፈጠረው ስምጥ ኳታር ቁልፍ አደራዳሪ ሆና አገልግላለች። ስልጣን ከመልቀቃቸው በፊትም በአሜሪካ ጥያቄ መሰረት ታሊባን በኳታር ጽህፈት ቤት እንዲከፍት አድርገዋል፤ ይህም በመጨረሻ ኔቶ እና አሜሪካ በ2021 ከአፍጋኒስታን ለወጡበት ታሪካዊ ድርድር በር ከፋች ሆኖ አልፏል።
በአረብ ጸደይ ወቅት ኳታር ከህዝባዊ አመጾች ጎን ከቆሙ ጥቂት ሀገራት አንዷ ነበረች። በግብፅ፣ አልጀዚራ የስርጭት እገዳን ጥሶ የዲሞክራሲ ደጋፊዎችን ድምፅ ለዓለም አሰምቷል። በሶሪያ፣ ሼክ ሐማድ መጀመሪያ ላይ ፕሬዝዳንት ባሻር አል አሳድ ስልጣን እንዲለቁ ለማሳመን ቢሞክሩም፣ የመንግስት ኃይሎች ሰልፈኞችን መግደላቸውን ተከትሎ ዶሃ ከደማስቆ ጋር ያላትን ግንኙነት አቋርጣለች። በሊቢያ ደግሞ የረጅም ጊዜ መሪ የነበሩትን ሙአመር ጋዳፊን ከስልጣን ያወረደውን የኔቶ ወታደራዊ ዘመቻ በመደገፍ ኳታር ትልቅ ሚና ተጫውታለች።
እ.ኤ.አ ሰኔ 25፣ 2013 ሼክ ሐማድ ባልተለመደ ሁኔታ እና በፍጹም ፈቃደኝነት ስልጣናቸውን ለ33 ዓመቱ ልጃቸው ለሼክ ታሚም ቢን ሐማድ አል ታኒ አስረከቡ። እንዲህ ዓይነቱ ሰላማዊ የስልጣን ሽግግር በመካከለኛው ምስራቅ እጅግ ያልተለመደ እና ብርቅ ክስተት ነበር። ስልጣን ሲለቁም "ወጣቱ አመራር ባንዲራውን ከፍ አድርጎ ወደሚያውለበልብበት አዲስ ዘመን ስትገቡ፣ የወደፊቱ ጊዜ በፊታችሁ አለ" በማለት ለሀገሪቱ ልጆች ተስፋ ሰጥተዋል።
ከሁሉም በላይ ግን ለልባቸው እጅግ ቅርብ የነበረው የፍልስጤም የነጻነት ትግል ነው። ከዓመታት በኋላ የጋዛ ሰርጥን በመጎብኘት የመጀመሪያው የሀገር መሪ የሆኑት እሳቸው ነበሩ። ለፍልስጤም ህዝብ ላደረጉት ድጋፍ ክብር ሲባል፣ በጋዛ እና በደቡብ ሊባኖስ የሚገኙ ከተሞች በስማቸው ተሰይመዋል። ሼክ ሐማድ ቢን ኻሊፋ አል ታኒ ያሳደሩት ተጽዕኖ ከኳታር ድንበር እጅግ የራቀ ነበር፤ ህልፈታቸውም ልክ እንደ ህይወት ዘመናቸው ሁሉ በመላው ቀጠናው እና ከዚያም ባለፈ በዓለም ዙሪያ በጥልቅ የሚታወስ ይሆናል።
እ.ኤ.አ በጥር 1952 በዶሃ የተወለዱት ሼክ ሐማድ፣ ከብሪታንያው ሮያል ሚሊተሪ አካዳሚ ከተመረቁ በኋላ የኳታር የጦር ኃይሎች አዛዥ በመሆን አገልግለዋል። በ1977 አልጋ ወራሽ እና የመከላከያ ሚኒስትር ሆነው የተሾሙ ሲሆን፣ በሰኔ 27፣ 1995 ደግሞ የሀገሪቱን የስልጣን መንበር በይፋ ተረከቡ። ወደ ስልጣን ከመጡበት ጊዜ አንስቶ ሀገራቸው ያላትን እጅግ ሰፊ የተፈጥሮ ጋዝ ሀብት በመጠቀም ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ ማሻሻያዎችን ያካተተ ትልቅ የልማት ራዕይ ነድፈው በተግባር አሳይተዋል።
በሳቸው የስልጣን ዘመን የኳታር አጠቃላይ የሀገር ውስጥ ምርት (GDP) ከ24 እጥፍ በላይ በሚያስገርም ፍጥነት አድጓል። በተለይም ከኖርዝ ፊልድ የተገኘው ምርት፣ ኳታርን እ.ኤ.አ በ2006 የዓለማችን ትልቋ የፈሳሽ የተፈጥሮ ጋዝ (LNG) ላኪ ሀገር እንድትሆን አድርጓታል። በመንግስት መረጃ መሰረት... ይህች ትንሽ ሀገር በአጭር ጊዜ ውስጥ የማምረት አቅሟን በዓመት ወደ 77 ሚሊዮን ቶን ማድረስ ችላ ነበር።
የሼክ ሐማድ የአመራር ዘመን በለውጥ የተሞላ ነበር። የኳታር ፋውንዴሽን መመስረት፣ በ1996 የዓለምን የሚዲያ ትኩረት የሳበው የአልጀዚራ የዜና ቻናል መከፈት፣ በ2004 የመጀመሪያው ቋሚ የኳታር ህገ-መንግስት መጽደቅ እና ሴቶች የመምረጥና የመመረጥ መብት ያገኙበት የማዘጋጃ ቤት ምርጫ መጀመር የሳቸው ትሩፋቶች ናቸው። ከዚህም በላይ ኳታር በ2022ቱን የፊፋ ዓለም ዋንጫ የማስተናገድ መብት እንድታገኝ ያደረጉት ጥረት፣ አንዲት አረብ ሀገር ይህንን ታላቅ ውድድር ስታስተናግድ በታሪክ የመጀመሪያው እንዲሆን አስችሏል።
ሼክ ሐማድ ኳታርን የዓለም አቀፍ ዲፕሎማሲ ማዕከል እና የሰላም አደራዳሪ እንድትሆን ሰፊ ራዕይ ነበራቸው። በሱዳን ዳርፉር ክልል፣ በሊባኖስ የውስጥ ትርምስ፣ እንዲሁም በፍልስጤሙ ሃማስ እና ፋታህ መካከል ለተፈጠረው ስምጥ ኳታር ቁልፍ አደራዳሪ ሆና አገልግላለች። ስልጣን ከመልቀቃቸው በፊትም በአሜሪካ ጥያቄ መሰረት ታሊባን በኳታር ጽህፈት ቤት እንዲከፍት አድርገዋል፤ ይህም በመጨረሻ ኔቶ እና አሜሪካ በ2021 ከአፍጋኒስታን ለወጡበት ታሪካዊ ድርድር በር ከፋች ሆኖ አልፏል።
በአረብ ጸደይ ወቅት ኳታር ከህዝባዊ አመጾች ጎን ከቆሙ ጥቂት ሀገራት አንዷ ነበረች። በግብፅ፣ አልጀዚራ የስርጭት እገዳን ጥሶ የዲሞክራሲ ደጋፊዎችን ድምፅ ለዓለም አሰምቷል። በሶሪያ፣ ሼክ ሐማድ መጀመሪያ ላይ ፕሬዝዳንት ባሻር አል አሳድ ስልጣን እንዲለቁ ለማሳመን ቢሞክሩም፣ የመንግስት ኃይሎች ሰልፈኞችን መግደላቸውን ተከትሎ ዶሃ ከደማስቆ ጋር ያላትን ግንኙነት አቋርጣለች። በሊቢያ ደግሞ የረጅም ጊዜ መሪ የነበሩትን ሙአመር ጋዳፊን ከስልጣን ያወረደውን የኔቶ ወታደራዊ ዘመቻ በመደገፍ ኳታር ትልቅ ሚና ተጫውታለች።
እ.ኤ.አ ሰኔ 25፣ 2013 ሼክ ሐማድ ባልተለመደ ሁኔታ እና በፍጹም ፈቃደኝነት ስልጣናቸውን ለ33 ዓመቱ ልጃቸው ለሼክ ታሚም ቢን ሐማድ አል ታኒ አስረከቡ። እንዲህ ዓይነቱ ሰላማዊ የስልጣን ሽግግር በመካከለኛው ምስራቅ እጅግ ያልተለመደ እና ብርቅ ክስተት ነበር። ስልጣን ሲለቁም "ወጣቱ አመራር ባንዲራውን ከፍ አድርጎ ወደሚያውለበልብበት አዲስ ዘመን ስትገቡ፣ የወደፊቱ ጊዜ በፊታችሁ አለ" በማለት ለሀገሪቱ ልጆች ተስፋ ሰጥተዋል።
ከሁሉም በላይ ግን ለልባቸው እጅግ ቅርብ የነበረው የፍልስጤም የነጻነት ትግል ነው። ከዓመታት በኋላ የጋዛ ሰርጥን በመጎብኘት የመጀመሪያው የሀገር መሪ የሆኑት እሳቸው ነበሩ። ለፍልስጤም ህዝብ ላደረጉት ድጋፍ ክብር ሲባል፣ በጋዛ እና በደቡብ ሊባኖስ የሚገኙ ከተሞች በስማቸው ተሰይመዋል። ሼክ ሐማድ ቢን ኻሊፋ አል ታኒ ያሳደሩት ተጽዕኖ ከኳታር ድንበር እጅግ የራቀ ነበር፤ ህልፈታቸውም ልክ እንደ ህይወት ዘመናቸው ሁሉ በመላው ቀጠናው እና ከዚያም ባለፈ በዓለም ዙሪያ በጥልቅ የሚታወስ ይሆናል።
2 months ago
የአራጣ ብድር ምንነት እና ተጠያቂነት
በኢትዮጵያ ህግ ማእቀፍ
ፋንታሁን ደለለው ጠበቃና የህግ አማካሪ
መግቢያ #ethiopia | የአራጣ ብድር በኢ.ፌ.ዲ.ሪ የወንጀል ሕግ የህሊናን ወይም የሰውን ችግር መሰረት በማድረግ የሚፈፀሙ ወንጀሎች ስር የሚካትት ወንጀል ሲሆን አስቀጪነቱም በሕጉ ተደንግጓል። ይህ ድርጊት በማኅበረሰብ ላይ መጠነ ሰፊ ጉዳት የሚያደርስ በመሆኑ በሕግም ሆነ በሞራል ተቀባይነት የሌለው ተግባር ነው። በዚህ ጽሑፍ የአራጣን ምንነት፣ በሕግ የተፈቀደን የወለድ መጠን፣ የአራጣ መንስኤዎችንና የሚያስከትላቸውን ጉዳቶች እና የአራጣ ብድር ተጠያቂነት እና መፍትሄዎችን ጭምር በአጭሩ እንዳስሳለን።
1. የአራጣ ምንነት
የሕግ መዝገበ ቃላት የሆነው ብላክስ ሎው መዝገበ ቃላት 8ኛው እትም እንደሚሰጠው ትርጉም ”USURY is an illegal contract for a loan or forbearance of money, goods, or things in action, by which illegal interest is reserved, or agreed to be reserved or taken.” ይህን ወደ አማርኛ በግርድፉ ስንመልሰው አራጣ ማለት ሕገ-ወጥ በሆነ የብድር ውል ወይም ገንዘብን፣ እቃዎችን ወይም በድርጊት ላይ ያሉ ነገሮችን መስጠት ሆኖ ሕጋዊ ያልሆነ ወለድ ለመጠበቅ ወይም ለመስጠት የሚደረግ ስምምነት ነው። በሌላ በኩል ማሪያም ዌብስተር የተሰኘው መዝገበ ቃላት አራጣን በተጋነነ የወለድ መጠን ገንዘብ ማበደር በማለት ይተረጉመዋል። በመሆኑም ከተለያዩ ትርጉሞች መረዳት እንደሚቻለው አራጣ ያልተገባ የወለድ ስሌት ተበዳሪዎችን በማስከፈል የሚፈፀም ድርጊት ነው፡፡ ተመጣጣኝ የወለድ መጠን ፋይናንስ ገበያው ወይም ብሔራዊ ባንኮች በሚወስኑት መሰረት ማሰብ ተገቢ ቢሆነም በሕግ ከተወሰነው የወለድ ምጣኔ በላይ ገንዘብ ማበደር በብዙ አገሮች ዘንድ ወንጀል ተደርጎ ተደንግጓል፡፡ ወንጀሉም አራጣ በመባል ይታወቃል፡፡
በሀገራችን በ1996 ዓ.ም በወጣው የኢ.ፌ.ዲ.ሪ የወንጀል ሕግ ለአራጣ ቀጥተኛ ትርጉም ባይሰጥም በአንቀጽ 712 በአራጣ ወንጀል የሚያስጠይቁ ተግባራትን ያስቀምጣል። ይኸውም ማንም ሰው የተበዳዩን ችግረኝነት፣ የበታችነቱን፣ ወይም የገንዘብ ችግሩን፣ ወይም መንፈሰ ደካማነቱን፣ ወይም ልምድ ወይም ችሎታ የሌለው መሆኑን መሰረት በማድረግ፡-
በሕግ ከተፈቀደው ወለድ በላይ ገንዘብ ያበደረው እንደሆነ ወይም
ካበደረው ገንዘብ ጋራ በግልፅ ተመጣጣኝነት የሌለው ንብረት በምትኩ እንዲሰጠው ያደረገው ወይም ቃል ያስገባው እንደሆነ የአራጣ ወንጀል በመፈፀም የሕግ ተጠያቂነት ይኖርበታል።
በመሆኑም በአጠቃላይ አራጣ ማለት በሕግ ከተፈቀደው በላይ የተጋነነ የወለድ መጠን በማስከፈል እና ከገንዘቡ ጋር ተመጣጣኝነት የሌለው መያዣ በመቀበል የሚደረግ የብድር ስምምነት ሲሆን ይህም የተበዳሪውን ሁኔታ ማለትም ችግረኝነቱን፣ የበታችነቱን፣ የገንዘብ ችግሩን፣ መንፈሰ ደካማነቱን... መሠረት በማድረግ የሚፈፀም ብዝበዛ" (Exploitation of distress) ነው፡፡
በኢትዮጵያ በሕግ የተፈቀደውን የወለድ መጠን ስንመለከት የፍትሐብሔር ሕጉ ቁጥር 1751 ሕጋዊ ወለድ (Legal Rate of Interest) ማለት በውል ያልተወሰነ ወለድ (ጥቅም) ከፋይ የሆነ ሰው በዓመት በመቶ ዘጠኝ (9%) ሂሳብ ይከፍላል ይላል። በተጨማሪም የፍትሐብሔር ሕጉ ቁጥር 2479(1) የብድር ውል ተዋዋይ ወገኖች ተበዳሪው ሊከፍለው የሚገባው የወለድ መጠን በወር ወይም በቀን ሳይሆን በዓመት ከአስራ ሁለት በመቶ (12%) በላይ ሊበልጥ እንደማይችል ይደነግጋል፡፡ በመሆኑም ሕጉ የፈቀደው የብድር ውል ወለድ መጠን በዓመት 12% ድረስ ብቻ እንደሆነ መረዳት ይቻላል።
2. የኢፊድሪ ህግ 1996 እና የኢትዮጵያ ፍትሀብሄር ህግ ተፈጻሚነት ወሰን
ይሁንና ይህ የወለድ መጠን በባንኮች እና በማይክሮ ፋይናንስ ተቋማት ላይ ተፈፃሚነት የለውም። ምክንያቱም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የገንዘብ ብድር አቅርቦት በተፈለገው መጠን መገኘትን፣ እንዲሁም የወለድ ተመንና ሌሎች ክፍያዎችን የመወሰንና የመቆጣጠር ሥልጣን የተሰጠው ሲሆን ብሔራዊ ባንክ በአዋጅ ቁጥር 591/2000 ዓ.ም አንቀፅ 5(4) እና በመመሪያ ቁጥር 12/2010 መሠረት የብድር ውል ለደንበኞቻቸው በሚሰጡበት ወቅት ላበደሩት ብድር የወለዱን ምጣኔ በራሳቸው እንዲወስኑ ሥልጣን ተሰጥቷቸዋል፡፡ እንዲሁም በኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ የወለድ ተመን መመሪያ ቁጥር 295/2020 መሰረት በብድር እና በቅድመ ክፍያ ላይ የብድር መጠን በተመለከተ በእያንዳንዱ ባንክ በነፃነት የሚወሰን እንደሆነ ያስቀምጣል። በመሆኑም ባንኮች በሚሰጡት ብድር ላይ የሚታሰበው የወለድ ምጣኔ ከላይ በፍትሐብሔር ሕጉ እንደተመለከተው የወለድ ጣራው በዓመት እስከ 12% ብቻ ሳይሆን ከዛም በላይ ማድረግ ይችላሉ።
በዚሁ መሰረት የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከየካቲት 28 ቀን 2017 ዓ.ም. ጀምሮ ተግባራዊ የሚደረግ በተለያዩ የብድር ዓይነቶች ላይ ጭማሪ ያደረገ ሲሆን በተደረገው ማስተካከያ መሰረት፣ የግብርና ብድሮች እስከ 15.5%፣ የንግድ ብድሮች እስከ 18%፣ የወጪ ንግድ ብድሮች እስከ 14%፣ የግል ብድሮች ደግሞ እስከ 15% ጭማሪ ተደርጎባቸዋል። ስለዚህ አራጣ ማለት ሕጉ ከፈቀደው የብድር ወለድ መጠን በላይ ተዋውሎ ማበደር ማለት ነው፡፡
3. የአራጣ ወንጀል የሚያስከትላቸው ጉዳቶች
አራጣ በተበዳሪዎች ላይ ከፍተኛ ጉዳት ሊያስከትል ይችላል። ተበዳሪዎች ለተበደሩት ገንዘብ እንዲከፍሉ የሚጠየቁት የወለድ መጠኑ በጣም የተጋነነ ስለሆነ ብድሩን መልሰው ሳይጨርሱ ጥሪታቸው ወይም በብድሩ ገንዘብ ሰርተው ያገኙትን ትርፍ አበዳሪው ስለሚወስድባቸው ለኪሳራ እና ለከፋ ድህነት ይዳረጋሉ፡፡ ተበዳሪዎች ጊዜያዊ ችግሮችን ለመቅረፍ ብለው በተበደሩት ገንዘብ ድህነትን ሸምተዉ ድሀ ሆነው ሲቀሩ፤ አበዳሪዎችም ምንም እሴት በኢኮኖሚ ውስጥ ሳይጨምሩ ሀብት የሚሰበስቡበት ሁኔታ ይፈጥራል፡፡
የአራጣ ወንጀል በግለሰቦች ላይ ከሚያደርሰው ጉዳት ባለፈ የድርጊቱ መበራከት ሀገራዊ ጉዳት በማስከተል የሀገር ኢኮኖሚ ላይ ሊያደርስ የሚችለው ተፅዕኖ ቀላል የሚባል አይሆንም። በአራጣ የሚዘዋወረው ገንዘብ ላይ መንግሥት እውቅና ስለማይኖረው ከትርፉ ላይ ግብር ስለማይከፈል መንግሥት ገቢ ሳይሰበስብ ይቀራል፡፡
ሌላው ጉዳት ገንዘብ ያላቸው ሰዎች ገንዘባቸውን ባንክ እንዳያስቀምጡ ከማድረጉ ጋር የተያያዘ ሲሆን ይህም የሚሆነው ጥቂትም ቢሆን ገንዘብ ያላቸው ሰዎች ገንዘባቸውን ባንክ ከማስቀመጥ ይልቅ አራጣ በማበደር እንዲሰማሩ በማድረጉ ነው፡፡ ገንዘቡ በባንክ ተቀመምጦ ለኢኮኖሚው ሊያበረክተው የሚችለውን አስተዋጽኦ የሚያስቀረው ሲሆን ወደ ባንኮች የሚገባው ተቀማጭ እየቀነሰ መሄዱ በመጨራሻም ባንኮች አቅም እያጠራቸው እንዲሄዱ ያደርጋቸዋል፡፡ ባንኮች ለብድር የሚውል ተቀማጭ ገንዘብ ሲያጥራቸው በተዘዋዋሪ አራጣ አበዳሪዎች የብድር አማራጭ ይሆናሉ፡፡ ይህ መሆኑ ደግሞ በተመጣጣኝ ወለድ መጠን ገንዘብ ተበድረው ሥራ ሊሰሩ የሚችሉ ሰዎች ብድር ሳያገኙ እንዲቀሩ ያደርጋቸዋል።
4. የአራጣ ብድር ተጠያቂነት
በአራጣ ብድር በሚያስከትሉ የወንጀል እና የፍትሀብሄር ተጠያቂነትን በዚህ ክፍል ያካተትን ሲሆን እንደማከተለው ቀርቧል።
4.1 የአራጣ ወንጀል የሕግ ተጠያቂነት
የአራጣ ወንጀል በወንጀል ሕጉ በአንቀፅ 712 ስር ሽፋን አግኝቷል። ከላይ እንደተገለፀው በድንጋጌው ላይ የዘረዘሩትን ተግባራት የፈፀመ ሰው በቀላል እስራት ወይም እንደነገሩ ሁኔታ ከ5 (አምስት አመት) በማይበልጥ ፅኑ እስራት እና በመቀጮ ይቀጣል፡፡ በተመሳሳይ ሁኔታ ማንኛውም ሰው ከላይ በተጠቀሰው ሀሳብ መነሻነት በአራጣ ላይ የተመሰረተ መብት የተቀበለ፣ በመከላከያነት የተጠቀመበት ወይም ለሌላ ሰው ያስተላለፈ እንደሆነ በተመሳሳይ ሁኔታ ይቀጣል፡፡
4.2 የአራጣ ብድር የፍትሀብሄር ተጠያቂነት
በፍትሃብሔር ህግ አንቀጽ 1162 መሠረት አላግባብ መበልጸግ በፍትሃብሔር ቀጥታ ወይም በሌላ መንገድ በእርግጥ ተጎጂ የሆነው ሰው ወይም አካል የተበዳሪውን ችግር ውስጥ መግባት ወይም የመንፈስ/ስነ ልቦና ደካማናት በመጠቀም በማበደር ያልተገባ፣በህግ ያልተደገፈ የወለድ ምጣኔን በመተመን የሚያበድሩ አካላት በፍትሃብሔር ውል ህጎቻችን ቁጥር 1676 ጀምሮ እንደሚደነግገው ከፍቃድ ውጪ እንደሆነ ተቆጥሮ አላግባብ ጥቅም ለማግኘት ሲባል በህገወጥ ስምምነት/1808(2) መሠረት እንዳልነበረ ሊቆጠር የሚችል ወይም ሊፈርስ የሚችል ውል በመሆኑ ተበዳሪው ከተበደረው ክፍያ በላይ በአበዳሪው ተጠይቆ እንደሆነ ይህንን ሊያስመልስ መብት አለው።
5. የአራጣ ብድር ውል ጉዳቶች
5.1 አራጣ በተበዳሪዎች ላይ ከፍተኛ ጉዳት ሊያስከትል ይችላል። ተበዳሪዎች ለተበደሩት ገንዘብ እንዲከፍሉ የሚጠየቁት የወለድ መጠኑ በጣም የተጋነነ ስለሆነ ብድሩን መልሰው ሳይጨርሱ ጥሪታቸው ወይም በብድሩ ገንዘብ ሰርተው ያገኙትን ትርፍ አበዳሪው ስለሚወስድባቸው ለኪሳራ እና ለከፋ ድህነት ይዳረጋሉ፡፡ ተበዳሪዎች ጊዜያዊ ችግሮችን ለመቅረፍ ብለው በተበደሩት ገንዘብ ድህነትን ሸምተዉ ድሀ ሆነው ሲቀሩ፤ አበዳሪዎችም ምንም እሴት በኢኮኖሚ ውስጥ ሳይጨምሩ ሀብት የሚሰበስቡበት ሁኔታ ይፈጥራል፡፡
5.2 የአራጣ ወንጀል በግለሰቦች ላይ ከሚያደርሰው ጉዳት ባለፈ የድርጊቱ መበራከት ሀገራዊ ጉዳት በማስከተል የሀገር ኢኮኖሚ ላይ ሊያደርስ የሚችለው ተፅዕኖ ቀላል የሚባል አይሆንም። በአራጣ የሚዘዋወረው ገንዘብ ላይ መንግሥት እውቅና ስለማይኖረው ከትርፉ ላይ ግብር ስለማይከፈል መንግሥት ገቢ ሳይሰበስብ ይቀራል፡፡
5.3 ሌላው ጉዳት ገንዘብ ያላቸው ሰዎች ገንዘባቸውን ባንክ እንዳያስቀምጡ ከማድረጉ ጋር የተያያዘ ሲሆን ይህም የሚሆነው ጥቂትም ቢሆን ገንዘብ ያላቸው ሰዎች ገንዘባቸውን ባንክ ከማስቀመጥ ይልቅ አራጣ በማበደር እንዲሰማሩ በማድረጉ ነው፡፡ ገንዘቡ በባንክ ተቀመምጦ ለኢኮኖሚው ሊያበረክተው የሚችለውን አስተዋጽኦ የሚያስቀረው ሲሆን ወደ ባንኮች የሚገባው ተቀማጭ እየቀነሰ መሄዱ በመጨራሻም ባንኮች አቅም እያጠራቸው እንዲሄዱ ያደርጋቸዋል፡፡ ባንኮች ለብድር የሚውል ተቀማጭ ገንዘብ ሲያጥራቸው በተዘዋዋሪ አራጣ አበዳሪዎች የብድር አማራጭ ይሆናሉ፡፡ ይህ መሆኑ ደግሞ በተመጣጣኝ ወለድ መጠን ገንዘብ ተበድረው ሥራ ሊሰሩ የሚችሉ ሰዎች ብድር ሳያገኙ እንዲቀሩ ያደርጋቸዋል።
6. የህግ ምክር
ገንዘብ ተበዳሪዎች ወይም ፈላጊዎች ባስፈለጋቸው የኢንቨስትመንት ወይም የብድር አገልግሎት መስክ በመሰማራት ካልተፈለገ ጉዳትና ኪሳራ እንዲድኑ እንዲሁም በዘመነ የፋይናንስ ስረአት ለመመራት ፤ የፋይናንስ ተቋማት ብድር በተጠየቁ ጊዜ ቀልጣፋና፣ማራኪ በሆነ አገልግሎት የብድር አገልግሎት እንዲያቀርቡ የአሰራር ማሻሻል እንዲኖር ተገቢውን ጥረት ማድረግ እንዲሁም ለማህበረሰቡ ማለትም ለተበዳሪውም ሆነ ለአበዳሪው
አግባብ ያለው የህግ ግንዛቤ እንዲኖረው ማስቻል የሀገራችን ኢኮኖሚ እድገት እና ለዜጎች የነፍስ ወከፍ ገቢ መጨመር ከፍተኛ አስተዋጽኦ ይኖረዋል።
ማጣቀሻዎች/References/
1. የኢፊድሪ ወንጀል ህግ 1996
2. የኢትዮጵያ ፍተሀብሔር ህግ 1952
3. የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የተቋቋመበት አዋጅ ቁጥር 591/2002
4. የፍትህ ሚኒስተር የፊት /የፌስቡክ/ ገጽ
45 ሌሎች የባንክ ፥የማይክሮ ፋይናንስ አበዳሪ ተቋማት አዋጅ፣ደንብ፣መመሪያዎች
ጠበቃና የህግ አማካሪ ፋንታሁን ደለለው
https://t.me/Fantahunlawye...
0929101037
በኢትዮጵያ ህግ ማእቀፍ
ፋንታሁን ደለለው ጠበቃና የህግ አማካሪ
መግቢያ #ethiopia | የአራጣ ብድር በኢ.ፌ.ዲ.ሪ የወንጀል ሕግ የህሊናን ወይም የሰውን ችግር መሰረት በማድረግ የሚፈፀሙ ወንጀሎች ስር የሚካትት ወንጀል ሲሆን አስቀጪነቱም በሕጉ ተደንግጓል። ይህ ድርጊት በማኅበረሰብ ላይ መጠነ ሰፊ ጉዳት የሚያደርስ በመሆኑ በሕግም ሆነ በሞራል ተቀባይነት የሌለው ተግባር ነው። በዚህ ጽሑፍ የአራጣን ምንነት፣ በሕግ የተፈቀደን የወለድ መጠን፣ የአራጣ መንስኤዎችንና የሚያስከትላቸውን ጉዳቶች እና የአራጣ ብድር ተጠያቂነት እና መፍትሄዎችን ጭምር በአጭሩ እንዳስሳለን።
1. የአራጣ ምንነት
የሕግ መዝገበ ቃላት የሆነው ብላክስ ሎው መዝገበ ቃላት 8ኛው እትም እንደሚሰጠው ትርጉም ”USURY is an illegal contract for a loan or forbearance of money, goods, or things in action, by which illegal interest is reserved, or agreed to be reserved or taken.” ይህን ወደ አማርኛ በግርድፉ ስንመልሰው አራጣ ማለት ሕገ-ወጥ በሆነ የብድር ውል ወይም ገንዘብን፣ እቃዎችን ወይም በድርጊት ላይ ያሉ ነገሮችን መስጠት ሆኖ ሕጋዊ ያልሆነ ወለድ ለመጠበቅ ወይም ለመስጠት የሚደረግ ስምምነት ነው። በሌላ በኩል ማሪያም ዌብስተር የተሰኘው መዝገበ ቃላት አራጣን በተጋነነ የወለድ መጠን ገንዘብ ማበደር በማለት ይተረጉመዋል። በመሆኑም ከተለያዩ ትርጉሞች መረዳት እንደሚቻለው አራጣ ያልተገባ የወለድ ስሌት ተበዳሪዎችን በማስከፈል የሚፈፀም ድርጊት ነው፡፡ ተመጣጣኝ የወለድ መጠን ፋይናንስ ገበያው ወይም ብሔራዊ ባንኮች በሚወስኑት መሰረት ማሰብ ተገቢ ቢሆነም በሕግ ከተወሰነው የወለድ ምጣኔ በላይ ገንዘብ ማበደር በብዙ አገሮች ዘንድ ወንጀል ተደርጎ ተደንግጓል፡፡ ወንጀሉም አራጣ በመባል ይታወቃል፡፡
በሀገራችን በ1996 ዓ.ም በወጣው የኢ.ፌ.ዲ.ሪ የወንጀል ሕግ ለአራጣ ቀጥተኛ ትርጉም ባይሰጥም በአንቀጽ 712 በአራጣ ወንጀል የሚያስጠይቁ ተግባራትን ያስቀምጣል። ይኸውም ማንም ሰው የተበዳዩን ችግረኝነት፣ የበታችነቱን፣ ወይም የገንዘብ ችግሩን፣ ወይም መንፈሰ ደካማነቱን፣ ወይም ልምድ ወይም ችሎታ የሌለው መሆኑን መሰረት በማድረግ፡-
በሕግ ከተፈቀደው ወለድ በላይ ገንዘብ ያበደረው እንደሆነ ወይም
ካበደረው ገንዘብ ጋራ በግልፅ ተመጣጣኝነት የሌለው ንብረት በምትኩ እንዲሰጠው ያደረገው ወይም ቃል ያስገባው እንደሆነ የአራጣ ወንጀል በመፈፀም የሕግ ተጠያቂነት ይኖርበታል።
በመሆኑም በአጠቃላይ አራጣ ማለት በሕግ ከተፈቀደው በላይ የተጋነነ የወለድ መጠን በማስከፈል እና ከገንዘቡ ጋር ተመጣጣኝነት የሌለው መያዣ በመቀበል የሚደረግ የብድር ስምምነት ሲሆን ይህም የተበዳሪውን ሁኔታ ማለትም ችግረኝነቱን፣ የበታችነቱን፣ የገንዘብ ችግሩን፣ መንፈሰ ደካማነቱን... መሠረት በማድረግ የሚፈፀም ብዝበዛ" (Exploitation of distress) ነው፡፡
በኢትዮጵያ በሕግ የተፈቀደውን የወለድ መጠን ስንመለከት የፍትሐብሔር ሕጉ ቁጥር 1751 ሕጋዊ ወለድ (Legal Rate of Interest) ማለት በውል ያልተወሰነ ወለድ (ጥቅም) ከፋይ የሆነ ሰው በዓመት በመቶ ዘጠኝ (9%) ሂሳብ ይከፍላል ይላል። በተጨማሪም የፍትሐብሔር ሕጉ ቁጥር 2479(1) የብድር ውል ተዋዋይ ወገኖች ተበዳሪው ሊከፍለው የሚገባው የወለድ መጠን በወር ወይም በቀን ሳይሆን በዓመት ከአስራ ሁለት በመቶ (12%) በላይ ሊበልጥ እንደማይችል ይደነግጋል፡፡ በመሆኑም ሕጉ የፈቀደው የብድር ውል ወለድ መጠን በዓመት 12% ድረስ ብቻ እንደሆነ መረዳት ይቻላል።
2. የኢፊድሪ ህግ 1996 እና የኢትዮጵያ ፍትሀብሄር ህግ ተፈጻሚነት ወሰን
ይሁንና ይህ የወለድ መጠን በባንኮች እና በማይክሮ ፋይናንስ ተቋማት ላይ ተፈፃሚነት የለውም። ምክንያቱም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የገንዘብ ብድር አቅርቦት በተፈለገው መጠን መገኘትን፣ እንዲሁም የወለድ ተመንና ሌሎች ክፍያዎችን የመወሰንና የመቆጣጠር ሥልጣን የተሰጠው ሲሆን ብሔራዊ ባንክ በአዋጅ ቁጥር 591/2000 ዓ.ም አንቀፅ 5(4) እና በመመሪያ ቁጥር 12/2010 መሠረት የብድር ውል ለደንበኞቻቸው በሚሰጡበት ወቅት ላበደሩት ብድር የወለዱን ምጣኔ በራሳቸው እንዲወስኑ ሥልጣን ተሰጥቷቸዋል፡፡ እንዲሁም በኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ የወለድ ተመን መመሪያ ቁጥር 295/2020 መሰረት በብድር እና በቅድመ ክፍያ ላይ የብድር መጠን በተመለከተ በእያንዳንዱ ባንክ በነፃነት የሚወሰን እንደሆነ ያስቀምጣል። በመሆኑም ባንኮች በሚሰጡት ብድር ላይ የሚታሰበው የወለድ ምጣኔ ከላይ በፍትሐብሔር ሕጉ እንደተመለከተው የወለድ ጣራው በዓመት እስከ 12% ብቻ ሳይሆን ከዛም በላይ ማድረግ ይችላሉ።
በዚሁ መሰረት የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከየካቲት 28 ቀን 2017 ዓ.ም. ጀምሮ ተግባራዊ የሚደረግ በተለያዩ የብድር ዓይነቶች ላይ ጭማሪ ያደረገ ሲሆን በተደረገው ማስተካከያ መሰረት፣ የግብርና ብድሮች እስከ 15.5%፣ የንግድ ብድሮች እስከ 18%፣ የወጪ ንግድ ብድሮች እስከ 14%፣ የግል ብድሮች ደግሞ እስከ 15% ጭማሪ ተደርጎባቸዋል። ስለዚህ አራጣ ማለት ሕጉ ከፈቀደው የብድር ወለድ መጠን በላይ ተዋውሎ ማበደር ማለት ነው፡፡
3. የአራጣ ወንጀል የሚያስከትላቸው ጉዳቶች
አራጣ በተበዳሪዎች ላይ ከፍተኛ ጉዳት ሊያስከትል ይችላል። ተበዳሪዎች ለተበደሩት ገንዘብ እንዲከፍሉ የሚጠየቁት የወለድ መጠኑ በጣም የተጋነነ ስለሆነ ብድሩን መልሰው ሳይጨርሱ ጥሪታቸው ወይም በብድሩ ገንዘብ ሰርተው ያገኙትን ትርፍ አበዳሪው ስለሚወስድባቸው ለኪሳራ እና ለከፋ ድህነት ይዳረጋሉ፡፡ ተበዳሪዎች ጊዜያዊ ችግሮችን ለመቅረፍ ብለው በተበደሩት ገንዘብ ድህነትን ሸምተዉ ድሀ ሆነው ሲቀሩ፤ አበዳሪዎችም ምንም እሴት በኢኮኖሚ ውስጥ ሳይጨምሩ ሀብት የሚሰበስቡበት ሁኔታ ይፈጥራል፡፡
የአራጣ ወንጀል በግለሰቦች ላይ ከሚያደርሰው ጉዳት ባለፈ የድርጊቱ መበራከት ሀገራዊ ጉዳት በማስከተል የሀገር ኢኮኖሚ ላይ ሊያደርስ የሚችለው ተፅዕኖ ቀላል የሚባል አይሆንም። በአራጣ የሚዘዋወረው ገንዘብ ላይ መንግሥት እውቅና ስለማይኖረው ከትርፉ ላይ ግብር ስለማይከፈል መንግሥት ገቢ ሳይሰበስብ ይቀራል፡፡
ሌላው ጉዳት ገንዘብ ያላቸው ሰዎች ገንዘባቸውን ባንክ እንዳያስቀምጡ ከማድረጉ ጋር የተያያዘ ሲሆን ይህም የሚሆነው ጥቂትም ቢሆን ገንዘብ ያላቸው ሰዎች ገንዘባቸውን ባንክ ከማስቀመጥ ይልቅ አራጣ በማበደር እንዲሰማሩ በማድረጉ ነው፡፡ ገንዘቡ በባንክ ተቀመምጦ ለኢኮኖሚው ሊያበረክተው የሚችለውን አስተዋጽኦ የሚያስቀረው ሲሆን ወደ ባንኮች የሚገባው ተቀማጭ እየቀነሰ መሄዱ በመጨራሻም ባንኮች አቅም እያጠራቸው እንዲሄዱ ያደርጋቸዋል፡፡ ባንኮች ለብድር የሚውል ተቀማጭ ገንዘብ ሲያጥራቸው በተዘዋዋሪ አራጣ አበዳሪዎች የብድር አማራጭ ይሆናሉ፡፡ ይህ መሆኑ ደግሞ በተመጣጣኝ ወለድ መጠን ገንዘብ ተበድረው ሥራ ሊሰሩ የሚችሉ ሰዎች ብድር ሳያገኙ እንዲቀሩ ያደርጋቸዋል።
4. የአራጣ ብድር ተጠያቂነት
በአራጣ ብድር በሚያስከትሉ የወንጀል እና የፍትሀብሄር ተጠያቂነትን በዚህ ክፍል ያካተትን ሲሆን እንደማከተለው ቀርቧል።
4.1 የአራጣ ወንጀል የሕግ ተጠያቂነት
የአራጣ ወንጀል በወንጀል ሕጉ በአንቀፅ 712 ስር ሽፋን አግኝቷል። ከላይ እንደተገለፀው በድንጋጌው ላይ የዘረዘሩትን ተግባራት የፈፀመ ሰው በቀላል እስራት ወይም እንደነገሩ ሁኔታ ከ5 (አምስት አመት) በማይበልጥ ፅኑ እስራት እና በመቀጮ ይቀጣል፡፡ በተመሳሳይ ሁኔታ ማንኛውም ሰው ከላይ በተጠቀሰው ሀሳብ መነሻነት በአራጣ ላይ የተመሰረተ መብት የተቀበለ፣ በመከላከያነት የተጠቀመበት ወይም ለሌላ ሰው ያስተላለፈ እንደሆነ በተመሳሳይ ሁኔታ ይቀጣል፡፡
4.2 የአራጣ ብድር የፍትሀብሄር ተጠያቂነት
በፍትሃብሔር ህግ አንቀጽ 1162 መሠረት አላግባብ መበልጸግ በፍትሃብሔር ቀጥታ ወይም በሌላ መንገድ በእርግጥ ተጎጂ የሆነው ሰው ወይም አካል የተበዳሪውን ችግር ውስጥ መግባት ወይም የመንፈስ/ስነ ልቦና ደካማናት በመጠቀም በማበደር ያልተገባ፣በህግ ያልተደገፈ የወለድ ምጣኔን በመተመን የሚያበድሩ አካላት በፍትሃብሔር ውል ህጎቻችን ቁጥር 1676 ጀምሮ እንደሚደነግገው ከፍቃድ ውጪ እንደሆነ ተቆጥሮ አላግባብ ጥቅም ለማግኘት ሲባል በህገወጥ ስምምነት/1808(2) መሠረት እንዳልነበረ ሊቆጠር የሚችል ወይም ሊፈርስ የሚችል ውል በመሆኑ ተበዳሪው ከተበደረው ክፍያ በላይ በአበዳሪው ተጠይቆ እንደሆነ ይህንን ሊያስመልስ መብት አለው።
5. የአራጣ ብድር ውል ጉዳቶች
5.1 አራጣ በተበዳሪዎች ላይ ከፍተኛ ጉዳት ሊያስከትል ይችላል። ተበዳሪዎች ለተበደሩት ገንዘብ እንዲከፍሉ የሚጠየቁት የወለድ መጠኑ በጣም የተጋነነ ስለሆነ ብድሩን መልሰው ሳይጨርሱ ጥሪታቸው ወይም በብድሩ ገንዘብ ሰርተው ያገኙትን ትርፍ አበዳሪው ስለሚወስድባቸው ለኪሳራ እና ለከፋ ድህነት ይዳረጋሉ፡፡ ተበዳሪዎች ጊዜያዊ ችግሮችን ለመቅረፍ ብለው በተበደሩት ገንዘብ ድህነትን ሸምተዉ ድሀ ሆነው ሲቀሩ፤ አበዳሪዎችም ምንም እሴት በኢኮኖሚ ውስጥ ሳይጨምሩ ሀብት የሚሰበስቡበት ሁኔታ ይፈጥራል፡፡
5.2 የአራጣ ወንጀል በግለሰቦች ላይ ከሚያደርሰው ጉዳት ባለፈ የድርጊቱ መበራከት ሀገራዊ ጉዳት በማስከተል የሀገር ኢኮኖሚ ላይ ሊያደርስ የሚችለው ተፅዕኖ ቀላል የሚባል አይሆንም። በአራጣ የሚዘዋወረው ገንዘብ ላይ መንግሥት እውቅና ስለማይኖረው ከትርፉ ላይ ግብር ስለማይከፈል መንግሥት ገቢ ሳይሰበስብ ይቀራል፡፡
5.3 ሌላው ጉዳት ገንዘብ ያላቸው ሰዎች ገንዘባቸውን ባንክ እንዳያስቀምጡ ከማድረጉ ጋር የተያያዘ ሲሆን ይህም የሚሆነው ጥቂትም ቢሆን ገንዘብ ያላቸው ሰዎች ገንዘባቸውን ባንክ ከማስቀመጥ ይልቅ አራጣ በማበደር እንዲሰማሩ በማድረጉ ነው፡፡ ገንዘቡ በባንክ ተቀመምጦ ለኢኮኖሚው ሊያበረክተው የሚችለውን አስተዋጽኦ የሚያስቀረው ሲሆን ወደ ባንኮች የሚገባው ተቀማጭ እየቀነሰ መሄዱ በመጨራሻም ባንኮች አቅም እያጠራቸው እንዲሄዱ ያደርጋቸዋል፡፡ ባንኮች ለብድር የሚውል ተቀማጭ ገንዘብ ሲያጥራቸው በተዘዋዋሪ አራጣ አበዳሪዎች የብድር አማራጭ ይሆናሉ፡፡ ይህ መሆኑ ደግሞ በተመጣጣኝ ወለድ መጠን ገንዘብ ተበድረው ሥራ ሊሰሩ የሚችሉ ሰዎች ብድር ሳያገኙ እንዲቀሩ ያደርጋቸዋል።
6. የህግ ምክር
ገንዘብ ተበዳሪዎች ወይም ፈላጊዎች ባስፈለጋቸው የኢንቨስትመንት ወይም የብድር አገልግሎት መስክ በመሰማራት ካልተፈለገ ጉዳትና ኪሳራ እንዲድኑ እንዲሁም በዘመነ የፋይናንስ ስረአት ለመመራት ፤ የፋይናንስ ተቋማት ብድር በተጠየቁ ጊዜ ቀልጣፋና፣ማራኪ በሆነ አገልግሎት የብድር አገልግሎት እንዲያቀርቡ የአሰራር ማሻሻል እንዲኖር ተገቢውን ጥረት ማድረግ እንዲሁም ለማህበረሰቡ ማለትም ለተበዳሪውም ሆነ ለአበዳሪው
አግባብ ያለው የህግ ግንዛቤ እንዲኖረው ማስቻል የሀገራችን ኢኮኖሚ እድገት እና ለዜጎች የነፍስ ወከፍ ገቢ መጨመር ከፍተኛ አስተዋጽኦ ይኖረዋል።
ማጣቀሻዎች/References/
1. የኢፊድሪ ወንጀል ህግ 1996
2. የኢትዮጵያ ፍተሀብሔር ህግ 1952
3. የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የተቋቋመበት አዋጅ ቁጥር 591/2002
4. የፍትህ ሚኒስተር የፊት /የፌስቡክ/ ገጽ
45 ሌሎች የባንክ ፥የማይክሮ ፋይናንስ አበዳሪ ተቋማት አዋጅ፣ደንብ፣መመሪያዎች
ጠበቃና የህግ አማካሪ ፋንታሁን ደለለው
https://t.me/Fantahunlawye...
0929101037
2 months ago
ቀኝ አዝማች በኩረ ምዕመናን ትዛዙ ኮሬ የኢትዮጵያን ባህል፣ ቱሪዝምና በጎ አድራጎት በማስፋፋት የሚታወቁ ታዋቂ ኢንተርፕረነር፣ የባህል አምባሳደር እና ሀገር በቀል ሽማግሌ ናቸው። በተለይም በኢትዮጵያ የመጀመሪያዎቹን እና ግዙፍ የባህል ምግብ ቤቶች አንዱ የሆነውን ዮድ አቢሲኒያ (Yod Abyssinia) ባህላዊ ምግብ ቤት በመመስረታቸው በሰፊው ይታወቃሉ።
ስለ ቀኝ አዝማች ትዛዙ ኮሬ ዋና ዋና መረጃዎች
የዮድ አቢሲኒያ መስራችና ባለቤት በ1996 ዓ.ም.
(እ.ኤ.አ. በ2003) ዮድ አቢሲኒያ ባህላዊ ምግብ ቤትን መስርተዋል።
ምግብ ቤቱ የኢትዮጵያን ብሔር ብሔረሰቦች ባህላዊ ምግቦች፣ ሙዚቃዎች እና ውዝዋዜዎች ለአገር ውስጥና ለውጭ አገር ዜጎች በማስተዋወቅ ረገድ ትልቅ ሚና አለው።
እንደ የካናዳው ጠቅላይ ሚኒስትር ጀስቲን ትሩዶ ያሉ በርካታ የዓለም መሪዎችን እና የውጭ አገር ዲፕሎማቶችን በምግብ ቤታቸው አስተናግደዋል።
❸ማኅበራዊ አገልግሎትና የበጎ አድራጎት ሥራዎች
ማኅበራዊ አገልግሎትና የበጎ አድራጎት ሥራዎች
ለተለያዩ የሃይማኖት ተቋማት እና ችግረኛ ወገኖች ከፍተኛ ድጋፍ በማድረግ ይታወቃሉ።
በበጎ አድራጎት ሥራዎቻቸው ምክንያት በ2016 ዓ.ም የፊላንትሮፒ (የበጎ አድራጎት) ሽልማት አሸናፊ ሆነዋል።
በማኅበረሰቡ ውስጥ ሰላምን ለማስፈንና እርቅ ለማውረድ እንደ ትልቅ የሀገር ሽማግሌ ሆነው ያገለግላሉ።
በጎ ተግባራት እና ማህበራዊ ሀላፊነት በመወጣት አርዓያነት ያለዉን ተግባራት በመስራት ይታወቃል።
የዓመቱን 360 ቀናት ለኢትዮጵያ ሀገራቸዉ እንዲሁም 4 ቀናት ለበጎ አድራጎት ተግባራት ሲውል ፤ 365 ኛውን ቀን ደግሞ ዕድገት እንደሚያስተዋዉቅ የሚያምኑት የድርጅቱ መስራችና የቦርድ ሰብሳቢ ቀኝ አዝማች ትዛዙ ኮሬ ናቸዉ።
የዮድ አቢሲኒያ መስራችና የቦርድ ሰብሳቢ ቀኝ አዝማች ትዛዙ ኮሬ እንዲሁም ድርጅታቸዉ 'ዮድ አቢሲኒያ'ለመቄዶንያ የአረጋውያንና የአዕምሮ ህሙማን መርጃ ማህበር፣ ለሜሪጆይ ኢትዮጵያ ፣ ለቶራ የህፃናት ማሳደጊያ ፣ ለሰሊሆም የአእምሮ ህሙማን መርጃ ፣ ለየወደቁትን እናንሳ የአረጋውያን መርጃ ማህበር ለሌሎችም በማገዝና በመርዳት ማህበራዊ ኃላፊነትን በመወጣት በጎ ስምና አርዓያነትን በተግባር ለማሳየት ችሏል።ወደፊትም ይበልጥ ተጠናክሮ ይቀጥላል።
❹እዉቅናና ሽልማት
➢የዓመቱ በጎ ሰዉ ሽልማትና እዉቅና
ጳጉሜ 3 ቀን 2016 ዓ.ም ለ12ኛ ጊዜ በተካሄደዉ የዓመቱ በጎ ሰዉ ሽልማትና እዉቅና በቅርስ ባህል እና ቱሪዝም ዘርፍ ዮድ አቢሲኒያ፡የባሕል ምግብ አዳራሽ ተሸልሟል።
የኢትዮጵያን ባህላዊ ምግቦችን ፤ ውዝዋዜዎችን እና ባህላዊ እሴቶችን ለቱሪስቶች እና ማህበረሰቡ የሚያቀርብ ተቋም ሲሆን የኢትዮጵያን እሴቶችን በማስተዋወቅ ረገድ ያስቀመጠው ደማቅ አሻራ ከፍ ያለ ነዉ።
ዮድ አቢሲኒያ ባህል ባንድ
ለቱሪስቶች የአገራችንን ብሔር ብሔረሰቦች ሙዚቃዎች ዉዝዋዜን በማሳየት ቱባ ባህላችንን ሳይበረዝና ሳይከለስ ያሳያል።
➢ የቱሪዝም አዋርድ
የአዲስ አበባ ባህል፣ ኪነ-ጥበብና ቱሪዝም ቢሮ ሐምሌ 6/2016ዓ.ም በአድዋ መታሰብያ ሙዚየም ባካሄደው የኪነ-ጥበብና ቱሪዝም ትራንስፎርሜሽን ምክር ቤት ምስረታና 1ኛ መደበኛ ጉባኤ ለከተማችን የቱሪዝም ልማትና እድገት የላቀ አስተዋጽኦ ላደረጉ የቱሪዝም ተቋማትና አካላት የቱሪዝም አዋርድ ከተሰጡት መካከል አንዱ ዮድ አቢሲኒያ የባህል ምግብ አዳራሽ ነዉ።
የቱሪዝም ተቋማቱ በሚሰጡት የአገልግሎት ጥራት ባላቸው የቱሪዝም ፈጠራ ስራ እንዲሁም የቱሪስት አያያዝና የመሳሰሉት መስፈርቶችን መነሻ በማድረግ ከዘርፉ 1ኛ በመዉጣት ዮድ አቢሲኒያ የባህል ምግብ አዳራሽ፣የቱሪዝም አዋርድ ተሸልሟል።
➢"የ8ኛዉ የአርአያ ሰው ሽልማት"
ተቀማጭነቱን በሀገረ አሜሪካ ዳላስ ቴክሳስ ያደረገው ዓድዋ የባህልና የታሪክ ኅብረት ለትርፍ ያልተቋቋመ ግብረ ሰናይ ድርጅት ሲሆን በዋናነትም ለኢትዮጵያና ለኢትዮጵያውያን አርአያ የሚሆን ሥራ ለሚሠሩ ግለሰቦችና ተቋማት"የአርአያ ሰው ሽልማት" በሚል ዕውቅና ይሰጣል፡፡
ለ8ኛ ግዜ በአዲስ አበባ ዮድ አቢሲኒያ የባህል አዳራሽ ሰኔ 13 ቀን 2016 ዓ.ም በተመሳሳይ መልኩ ለሀገር ባለውለታዎች በተለይም በባህል ልማት፣ በተፈጥሮ ጥበቃ፣ በቱሪዝም እና ቅርስ እንዲሁም በታሪክ መስኮች ለሀገራቸው አስተዋጽኦ ላበረከቱ ግለሰቦችና ተቋማት ሽልማት ከተሰጣቸው መካከል ዮድ አቢሲኒያ የባህል ምግብ አዳራሽ አንዱ ነዉ።
ዓለም አቀፍ እውቅና
የኢትዮጵያን ባህልና ቱሪዝም በዓለም አቀፍ ደረጃ በማስተዋወቃቸው “የባህልና ቱሪዝም አምባሳደር” የሚል ክብር ተሰጥቷቸዋል።
በቅርቡ (እ.ኤ.አ በ2025) በአሜሪካ ሲያትል በተካሄደው የ42ኛው የኢትዮጵያውያን የስፖርትና ባህል ፌስቲቫል (ESFNA) ላይ ለሀገራቸው ላበረከቱት የላቀ አስተዋፅኦ ልዩ የክብር ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።
❺ዋና ዋና ቅርንጫፎችና አድራሻዎች
ዮድ አቢሲኒያ በአዲስ አበባ በተለያዩ ቁልፍ ቦታዎች ቅርንጫፎችን ከፍቶ ይገኛል፦
ቦሌ ቅርንጫፍ (ዋናው)፦ ቦሌ መድኃኔዓለም አካባቢ፣ ከብራስ ሆስፒታል ከፍ ብሎ የሚገኝ የነበረ ሲሆን አሁን ቀድሞ ከነበረበት በ100 ሜትር ገባ ብሎ ኬኬር ህንፃ አጠገብ ይገኛል።ለቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ቅርብ በመሆኑ ለቱሪስቶች ተመራጭ ነው።
ፒያሳ (ቴዎድሮስ አደባባይ) ቅርንጫፍ፦ በቅርቡ በዲል ፕላዛ ፊት ለፊት የተከፈተ አዲስና ዘመናዊ የባህል አዳራሽ፣ የስፖርት ባር (Sport Bar) እና የባዛር ማዕከል ነው።
ዮድ አቢሲኒያ ኢንተርናሽናል ሆቴል፦ ሰዓሊተ ምህረት አደባባይ ከፍ ብሎ፣ ወደ ወሰን በሚወስደው መንገድ ማዕድን ሚኒስቴር አጠገብ የሚገኝ ዘመናዊ ሆቴል ነው።
❻የ"ዮድ" መሪ ቃል በተግባር
የድርጅቱ መሪ ቃል የሃገራችን ኢትዮጵያን ”ባህል ፤ ታሪክ ፤ ቅርሶች እንጠብቅ፤ እናክብር ፤ ቋንቋችንን እናሳድግ ” የሚል ነው ባለፉት 22 ዓመታት የኢትዮጵያን ባህልና መስተንግዶን ጨምሮ ሲያስተዋውቅ ኖሯል ፡፡ ለዚህም አስተዋፅኦው ”የኢትዮጵያ የባህልና የቱሪዝም አምባሳደር” የሚል ዕውቅና ከመንግስት ተሰጥቶታል ፡፡
“ባህል ፤ ታሪክ ፤ ቅርሶች እንጠብቅ፤ እናክብር ፤ ቋንቋችንን እናሳድግ” በሚል መርህ ከመላው ዓለም ወደ ሃገራችን ለመጡ እንግዶች የባህል ምግብና መጠጦች መስተንግዶ በመስጠት ፣ የብሔር ብሄረሰቦችን ሙዚቃዎችና ውዝዋዜዎች በማቅረብ ፣ የሀገራችንን የታሪክ የባህልና የቱሪዝም ሃብቶችና ቅርሶቻችንን በማስተዋወቅ የኢትዮጵያን መልካም ገፅታ በመገንባት ብዙ በመስራት ”የኢትዮጵያ የባህል እና የቱሪዝም አምባሳደር” የሚል እውቅናን ለማግኘት ችሏል፡፡
"ዮድ"
ዮድ ብሂል የማነ እግዚአብሔር ገብረት ኃይለ
በእግዚአብሔር ቀኝ ያለ እሱ ኃያልና
ጽኑዕ የሆነ ነው ማለት በሌላ መልኩ"ዮድ" ማለት በጉራጌ ቋንቋ "መመስከር ወይም መናገር" ማለት ነዉ።
ከ1996ዓ.ምማለትምላለፉት 22 ዓመታት በተለያዩ ወቅቶች ወደ ሀገራችን የመጡ በርካታ የሀገራት መሪዎችን ፣ ዲፕሎማቶችን ፣ የዓለም ታላላቅ ሰዎችን፣ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት ፣ ታዋቂ ሰዎች ፣ ባለሀብቶች ፣ አትሌቶች ፣ አርቲስቶች የሚዲያ ባለሙያዎች እንዲሁም ሌሎችም በሺዎች የሚቆጠሩ ቱሪስቶችንና ኢትዮጵያዊያን እንግዶችን ተቀብሎ በፍቅርና በአክብሮት ሲያስተናግድ የቆየው ዮድ አቢሲኒያ በቀጣይም በሀገራችን ለሚከናወኑ ታላላቅ ሁነቶች ሙሉ አገልግሎት ለመስጠት ከወትሮው በተለዬ አኳኋን መዘጋጀቱ ተስተዉሏል።በ500 ብር ካፒታል እና በአነስተኛ የስራ ጅምር በጥረት የተገነባ ካምፓኒ በበርካታ ፈተናዎች ዉስጥ አልፎ ዛሬ በርካታ ቁጥር ላላቸዉ ወገኖቻችን የስራ ዕድል መፍጠር የቻለ ግዙፍ ኩባንያ ለመሆን በቅቷል።
"የሃገራችን ኢትዮጵያን ባህል ፤ ታሪክ ፤ ቅርሶች እንጠብቅ፤ እናክብር ፤ ቋንቋችንን እናሳድግ ”ዮድ አቢሲኒያ የባህል ምግብ አዳራሽ
ዘጋቢ ጋዜጠኛ ሲሳይ መንግስቴ
ስለ ቀኝ አዝማች ትዛዙ ኮሬ ዋና ዋና መረጃዎች
የዮድ አቢሲኒያ መስራችና ባለቤት በ1996 ዓ.ም.
(እ.ኤ.አ. በ2003) ዮድ አቢሲኒያ ባህላዊ ምግብ ቤትን መስርተዋል።
ምግብ ቤቱ የኢትዮጵያን ብሔር ብሔረሰቦች ባህላዊ ምግቦች፣ ሙዚቃዎች እና ውዝዋዜዎች ለአገር ውስጥና ለውጭ አገር ዜጎች በማስተዋወቅ ረገድ ትልቅ ሚና አለው።
እንደ የካናዳው ጠቅላይ ሚኒስትር ጀስቲን ትሩዶ ያሉ በርካታ የዓለም መሪዎችን እና የውጭ አገር ዲፕሎማቶችን በምግብ ቤታቸው አስተናግደዋል።
❸ማኅበራዊ አገልግሎትና የበጎ አድራጎት ሥራዎች
ማኅበራዊ አገልግሎትና የበጎ አድራጎት ሥራዎች
ለተለያዩ የሃይማኖት ተቋማት እና ችግረኛ ወገኖች ከፍተኛ ድጋፍ በማድረግ ይታወቃሉ።
በበጎ አድራጎት ሥራዎቻቸው ምክንያት በ2016 ዓ.ም የፊላንትሮፒ (የበጎ አድራጎት) ሽልማት አሸናፊ ሆነዋል።
በማኅበረሰቡ ውስጥ ሰላምን ለማስፈንና እርቅ ለማውረድ እንደ ትልቅ የሀገር ሽማግሌ ሆነው ያገለግላሉ።
በጎ ተግባራት እና ማህበራዊ ሀላፊነት በመወጣት አርዓያነት ያለዉን ተግባራት በመስራት ይታወቃል።
የዓመቱን 360 ቀናት ለኢትዮጵያ ሀገራቸዉ እንዲሁም 4 ቀናት ለበጎ አድራጎት ተግባራት ሲውል ፤ 365 ኛውን ቀን ደግሞ ዕድገት እንደሚያስተዋዉቅ የሚያምኑት የድርጅቱ መስራችና የቦርድ ሰብሳቢ ቀኝ አዝማች ትዛዙ ኮሬ ናቸዉ።
የዮድ አቢሲኒያ መስራችና የቦርድ ሰብሳቢ ቀኝ አዝማች ትዛዙ ኮሬ እንዲሁም ድርጅታቸዉ 'ዮድ አቢሲኒያ'ለመቄዶንያ የአረጋውያንና የአዕምሮ ህሙማን መርጃ ማህበር፣ ለሜሪጆይ ኢትዮጵያ ፣ ለቶራ የህፃናት ማሳደጊያ ፣ ለሰሊሆም የአእምሮ ህሙማን መርጃ ፣ ለየወደቁትን እናንሳ የአረጋውያን መርጃ ማህበር ለሌሎችም በማገዝና በመርዳት ማህበራዊ ኃላፊነትን በመወጣት በጎ ስምና አርዓያነትን በተግባር ለማሳየት ችሏል።ወደፊትም ይበልጥ ተጠናክሮ ይቀጥላል።
❹እዉቅናና ሽልማት
➢የዓመቱ በጎ ሰዉ ሽልማትና እዉቅና
ጳጉሜ 3 ቀን 2016 ዓ.ም ለ12ኛ ጊዜ በተካሄደዉ የዓመቱ በጎ ሰዉ ሽልማትና እዉቅና በቅርስ ባህል እና ቱሪዝም ዘርፍ ዮድ አቢሲኒያ፡የባሕል ምግብ አዳራሽ ተሸልሟል።
የኢትዮጵያን ባህላዊ ምግቦችን ፤ ውዝዋዜዎችን እና ባህላዊ እሴቶችን ለቱሪስቶች እና ማህበረሰቡ የሚያቀርብ ተቋም ሲሆን የኢትዮጵያን እሴቶችን በማስተዋወቅ ረገድ ያስቀመጠው ደማቅ አሻራ ከፍ ያለ ነዉ።
ዮድ አቢሲኒያ ባህል ባንድ
ለቱሪስቶች የአገራችንን ብሔር ብሔረሰቦች ሙዚቃዎች ዉዝዋዜን በማሳየት ቱባ ባህላችንን ሳይበረዝና ሳይከለስ ያሳያል።
➢ የቱሪዝም አዋርድ
የአዲስ አበባ ባህል፣ ኪነ-ጥበብና ቱሪዝም ቢሮ ሐምሌ 6/2016ዓ.ም በአድዋ መታሰብያ ሙዚየም ባካሄደው የኪነ-ጥበብና ቱሪዝም ትራንስፎርሜሽን ምክር ቤት ምስረታና 1ኛ መደበኛ ጉባኤ ለከተማችን የቱሪዝም ልማትና እድገት የላቀ አስተዋጽኦ ላደረጉ የቱሪዝም ተቋማትና አካላት የቱሪዝም አዋርድ ከተሰጡት መካከል አንዱ ዮድ አቢሲኒያ የባህል ምግብ አዳራሽ ነዉ።
የቱሪዝም ተቋማቱ በሚሰጡት የአገልግሎት ጥራት ባላቸው የቱሪዝም ፈጠራ ስራ እንዲሁም የቱሪስት አያያዝና የመሳሰሉት መስፈርቶችን መነሻ በማድረግ ከዘርፉ 1ኛ በመዉጣት ዮድ አቢሲኒያ የባህል ምግብ አዳራሽ፣የቱሪዝም አዋርድ ተሸልሟል።
➢"የ8ኛዉ የአርአያ ሰው ሽልማት"
ተቀማጭነቱን በሀገረ አሜሪካ ዳላስ ቴክሳስ ያደረገው ዓድዋ የባህልና የታሪክ ኅብረት ለትርፍ ያልተቋቋመ ግብረ ሰናይ ድርጅት ሲሆን በዋናነትም ለኢትዮጵያና ለኢትዮጵያውያን አርአያ የሚሆን ሥራ ለሚሠሩ ግለሰቦችና ተቋማት"የአርአያ ሰው ሽልማት" በሚል ዕውቅና ይሰጣል፡፡
ለ8ኛ ግዜ በአዲስ አበባ ዮድ አቢሲኒያ የባህል አዳራሽ ሰኔ 13 ቀን 2016 ዓ.ም በተመሳሳይ መልኩ ለሀገር ባለውለታዎች በተለይም በባህል ልማት፣ በተፈጥሮ ጥበቃ፣ በቱሪዝም እና ቅርስ እንዲሁም በታሪክ መስኮች ለሀገራቸው አስተዋጽኦ ላበረከቱ ግለሰቦችና ተቋማት ሽልማት ከተሰጣቸው መካከል ዮድ አቢሲኒያ የባህል ምግብ አዳራሽ አንዱ ነዉ።
ዓለም አቀፍ እውቅና
የኢትዮጵያን ባህልና ቱሪዝም በዓለም አቀፍ ደረጃ በማስተዋወቃቸው “የባህልና ቱሪዝም አምባሳደር” የሚል ክብር ተሰጥቷቸዋል።
በቅርቡ (እ.ኤ.አ በ2025) በአሜሪካ ሲያትል በተካሄደው የ42ኛው የኢትዮጵያውያን የስፖርትና ባህል ፌስቲቫል (ESFNA) ላይ ለሀገራቸው ላበረከቱት የላቀ አስተዋፅኦ ልዩ የክብር ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።
❺ዋና ዋና ቅርንጫፎችና አድራሻዎች
ዮድ አቢሲኒያ በአዲስ አበባ በተለያዩ ቁልፍ ቦታዎች ቅርንጫፎችን ከፍቶ ይገኛል፦
ቦሌ ቅርንጫፍ (ዋናው)፦ ቦሌ መድኃኔዓለም አካባቢ፣ ከብራስ ሆስፒታል ከፍ ብሎ የሚገኝ የነበረ ሲሆን አሁን ቀድሞ ከነበረበት በ100 ሜትር ገባ ብሎ ኬኬር ህንፃ አጠገብ ይገኛል።ለቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ቅርብ በመሆኑ ለቱሪስቶች ተመራጭ ነው።
ፒያሳ (ቴዎድሮስ አደባባይ) ቅርንጫፍ፦ በቅርቡ በዲል ፕላዛ ፊት ለፊት የተከፈተ አዲስና ዘመናዊ የባህል አዳራሽ፣ የስፖርት ባር (Sport Bar) እና የባዛር ማዕከል ነው።
ዮድ አቢሲኒያ ኢንተርናሽናል ሆቴል፦ ሰዓሊተ ምህረት አደባባይ ከፍ ብሎ፣ ወደ ወሰን በሚወስደው መንገድ ማዕድን ሚኒስቴር አጠገብ የሚገኝ ዘመናዊ ሆቴል ነው።
❻የ"ዮድ" መሪ ቃል በተግባር
የድርጅቱ መሪ ቃል የሃገራችን ኢትዮጵያን ”ባህል ፤ ታሪክ ፤ ቅርሶች እንጠብቅ፤ እናክብር ፤ ቋንቋችንን እናሳድግ ” የሚል ነው ባለፉት 22 ዓመታት የኢትዮጵያን ባህልና መስተንግዶን ጨምሮ ሲያስተዋውቅ ኖሯል ፡፡ ለዚህም አስተዋፅኦው ”የኢትዮጵያ የባህልና የቱሪዝም አምባሳደር” የሚል ዕውቅና ከመንግስት ተሰጥቶታል ፡፡
“ባህል ፤ ታሪክ ፤ ቅርሶች እንጠብቅ፤ እናክብር ፤ ቋንቋችንን እናሳድግ” በሚል መርህ ከመላው ዓለም ወደ ሃገራችን ለመጡ እንግዶች የባህል ምግብና መጠጦች መስተንግዶ በመስጠት ፣ የብሔር ብሄረሰቦችን ሙዚቃዎችና ውዝዋዜዎች በማቅረብ ፣ የሀገራችንን የታሪክ የባህልና የቱሪዝም ሃብቶችና ቅርሶቻችንን በማስተዋወቅ የኢትዮጵያን መልካም ገፅታ በመገንባት ብዙ በመስራት ”የኢትዮጵያ የባህል እና የቱሪዝም አምባሳደር” የሚል እውቅናን ለማግኘት ችሏል፡፡
"ዮድ"
ዮድ ብሂል የማነ እግዚአብሔር ገብረት ኃይለ
በእግዚአብሔር ቀኝ ያለ እሱ ኃያልና
ጽኑዕ የሆነ ነው ማለት በሌላ መልኩ"ዮድ" ማለት በጉራጌ ቋንቋ "መመስከር ወይም መናገር" ማለት ነዉ።
ከ1996ዓ.ምማለትምላለፉት 22 ዓመታት በተለያዩ ወቅቶች ወደ ሀገራችን የመጡ በርካታ የሀገራት መሪዎችን ፣ ዲፕሎማቶችን ፣ የዓለም ታላላቅ ሰዎችን፣ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት ፣ ታዋቂ ሰዎች ፣ ባለሀብቶች ፣ አትሌቶች ፣ አርቲስቶች የሚዲያ ባለሙያዎች እንዲሁም ሌሎችም በሺዎች የሚቆጠሩ ቱሪስቶችንና ኢትዮጵያዊያን እንግዶችን ተቀብሎ በፍቅርና በአክብሮት ሲያስተናግድ የቆየው ዮድ አቢሲኒያ በቀጣይም በሀገራችን ለሚከናወኑ ታላላቅ ሁነቶች ሙሉ አገልግሎት ለመስጠት ከወትሮው በተለዬ አኳኋን መዘጋጀቱ ተስተዉሏል።በ500 ብር ካፒታል እና በአነስተኛ የስራ ጅምር በጥረት የተገነባ ካምፓኒ በበርካታ ፈተናዎች ዉስጥ አልፎ ዛሬ በርካታ ቁጥር ላላቸዉ ወገኖቻችን የስራ ዕድል መፍጠር የቻለ ግዙፍ ኩባንያ ለመሆን በቅቷል።
"የሃገራችን ኢትዮጵያን ባህል ፤ ታሪክ ፤ ቅርሶች እንጠብቅ፤ እናክብር ፤ ቋንቋችንን እናሳድግ ”ዮድ አቢሲኒያ የባህል ምግብ አዳራሽ
ዘጋቢ ጋዜጠኛ ሲሳይ መንግስቴ
3 months ago
በሙስና የወንጀል ድርጊት የተከሰሱ በእስራት ተቀጡ
በፌዴሬሽን ምክር ቤት የሕገ መንግሥት ጉዳዮች የቀድሞ ዳይሬክተርን ጨምሮ 7 ግለሰቦች በተከሰሱበት የማይገባ ጥቅምን በማግኘት የወንጀል ድርጊት በእስራት ተቀጡ።
ግለሰቦቹ በዜግነት ኤርትራዊት የሆነች ግለሰብ ኢትዮጵያዊት ናት በማለት 400 ሚሊየን ብር የሚገመት ቤት እንድታገኝ ለማድረግ በመደራደራቸው ከ2 እስከ 7 ዓመት በሚደረስ ጽኑ እስራት እና በገንዘብ ቅጣት ተቀጥተዋል፡፡
ተከሳሾች 1ኛ አቶ ሙልዬ ወለላው የፌዴሬሽን ም/ቤት የህገ መንግሥት ትርጉምና የሕጎች ሕገ መንግሥታዊነት ክትትል ጉዳዮች ዳይሬክተር የነበረ፣ 2ኛ አቶ ኃ/ሚካኤል ልኬ የህግ አማካሪ እና ጠበቃ፣ 3ኛ አቶ ቃላት ባህታ በግል ስራ የሚተዳደርን ጨምሮ 7 ግለሰቦች ናቸው፡፡
በመጀመሪያ ክስ በ1ኛ፣ 2ኛ እና 3ኛ ተከሳሾች ላይ የቀረበ ሲሆን በ1996 ዓ.ም የወጣውን የወንጀል ሕግ አንቀጽ 32(1) (ሀ)፣ 33 እና የሙስና ወንጀሎችን ለመደንገግ የወጣውን አዋጅ ቁጥር 881/2007 አንቀጽ 9 (1) (ሀ) እና (2) ስር የተመለከተውን በመተላለፍ ነው፡፡
1ኛ ተከሳሽ ከ2ኛ እና 3ኛ ተከሳሾች ጋር በመመሳጠር የማይገባቸውን ጥቅም ለራሳቸው ለማግኘትና ለሌሎችም ለማስገኘት በማሰብ በኢትዮጵያና ኤርትራ መካከል ተከስቶ የነበረውን ግጭት ተከትሎ የሀገር ደህንነትን እና ህልውናን ለማስጠበቅ ሲባል ከሀገር የተሸኙ ኤርትራዊያን ንብረቶችን በጨረታ እንዲሸጥ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በሰጠው ትዕዛዝ መሰረት ከሀገር እንዲወጡ በተደረጉት ኤርትራዊ ቦሌ ክ/ከ ወረዳ 3 ስር የሚገኝ መኖርያ ቤት እና ይዞታ ለጨረታ እንዲቀርብ ተደርጎ 1ኛ የዐቃቤ ህግ ምስክር ወ/ሮ አልጋነሽ ኃይሉ የጨረታው አሸናፊ በመሆን በ1992 ዓ.ም የሽያጭ ውል በመፈፀም ቤቱን ከተረከቡ በኋላ ተከሳሾች በሀሰተኛ ደብዳቤው መነሻነት በዜግነት ኤርትራዊት የሆነችው 4ኛ ተከሳሽ ኢትዮጵያዊ ናት በሚል መደምደሚያ ላይ በመድረስ ውሉ ፈርሶ ቤቱን ወ/ሮ አልጋነሽ ኃይሉ ኤርትራዊት ለሆነችው 4ኛ ተከሳሽ ወ/ሮ ኤልሳቤት ተስፋጽዮን እንድታስረክብ በማለት የፌዴሬሽን ም/ቤት የወሰነውን ውሳኔ ድጋሚ ለምክር ቤቱ እንዳይቀርብ ለማድረግ በአካልና በስልክ በመገናኘትና በመደራደር፣ የዐቃቤ ህግ 1ኛ ምስክር ብር 400 ሚሊየን የሚገመት ቤትን እንዲያጡ አድርገዋል፡፡
በዚህም በዋና ወንጀል አድራጊነት በፈፀሙት ስልጣንን ያለአግባብ መገልገል ከባድ የሙስና ወንጀል መፈጸማቸውን ዐቃቤ ሕግ በክሱ ላይ ዘርዝሯል።
በሁተለኛ ክስ በተመሳሳይ1ኛ፣ 2ኛ፣ 5ኛ እና 6ኛ ተከሳሾች ከላይ በዝርዝር በተገለጸው የወንጀል ድርጊታቸው በህገ መንግሥት አጣሪ ጉባኤ በአብላጫው ድምጽ ትርጉም አያስፈልገውም በማለት በመወሰኑ በውሳኔው ቅር በመሰኘት የህገ መንግሥት ትርጉም ይሰጥልኝ ሲሉ ሕገ መንግሥት ትርጉም እንዲሰጣቸው ለፌዴሬሽን ም/ቤት የዕግድ እና የይግባኝ አቤቱታ በም/ቤቱ ተቀባይነት አግኝቶ ውሳኔው እንዳይቀየር በማድረግ ከፍተኛ ጥቅም ለማግኘት እና የግል ተበዳዮችን ይዞታ በማሳጣት ከፍተኛ የገንዘብ ጉዳት በማድረሳቸው 1ኛ እና 6ኛ ተከሳሾች በመንግሥት ወይም ህዝባዊ ድርጅት ሰራተኞች ብቻ በሚፈጸም የሙስና ወንጀል ውስጥ በልዩ ወንጀል አድራጊነት ተካፋይ ከሆኑት 2ኛ እና 5ኛ ተከሳሾች ጋር በዋና ወንጀል አድራጊነት ተካፋይ በመሆን በፈጸሙት የከባድ የስልጣን ያለአግባብ መገልገል ወንጀል ተከሰዋል፡፡
በሶስተኛ ክስ በ1ኛ እና 7ኛተከሳሾች 1ኛ ተከሳሽ በተጨማሪነት ለራሱም የማይገባውን 200 ሺህ ብር በማግኘቱ 1ኛ ተከሳሽ በመንግሥት ወይም ህዝባዊ ድርጅት ሰራተኞች ብቻ በሚፈጸም የሙስና ወንጀል ውስጥ በልዩ ወንጀል አድራጊነት ተካፋይ ከሆነው 7ኛ ተከሳሽ ጋር በዋና ወንጀል አድራጊነት ተካፋይ በመሆን በፈጸሙት በከባድ ስልጣንን አላግባብ መገልገል የሙስና ወንጀል የቅጣት ውሳኔ ተላልፎባቸዋል፡፡
ተከሳሾች ዛሬ የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 4ኛ የሙስና ጉዳዮች ወንጀል ችሎት በዋለዉ ችሎት 1ኛ ተከሳሽ በ6 ዓመት ከ4 ወር ጽኑ እስራት እና 3 ሺህ ብር፣ 2ኛ ተከሳሽ 2 ዓመት ከ8 ወር እና 5 ሺህ ብር፣ 3ኛ ተከሳሽ በቂ ማስረጃ ስላልተገኘበት በነጻ፣ 4ኛ ተከሳሽ 4 ዓመት ከ6 ወር፣ 5ኛ እና 6ኛ ተከሳሽ 2 ዓመት ከ8 ወር እና 1 ሺህ ብር እንዲሁም 7ኛ ተከሳሽ 7 ዓመት ከ6 ወር እና 10 ሺህ ብር እንዲቀጡ ወስኗል።
FBC
በፌዴሬሽን ምክር ቤት የሕገ መንግሥት ጉዳዮች የቀድሞ ዳይሬክተርን ጨምሮ 7 ግለሰቦች በተከሰሱበት የማይገባ ጥቅምን በማግኘት የወንጀል ድርጊት በእስራት ተቀጡ።
ግለሰቦቹ በዜግነት ኤርትራዊት የሆነች ግለሰብ ኢትዮጵያዊት ናት በማለት 400 ሚሊየን ብር የሚገመት ቤት እንድታገኝ ለማድረግ በመደራደራቸው ከ2 እስከ 7 ዓመት በሚደረስ ጽኑ እስራት እና በገንዘብ ቅጣት ተቀጥተዋል፡፡
ተከሳሾች 1ኛ አቶ ሙልዬ ወለላው የፌዴሬሽን ም/ቤት የህገ መንግሥት ትርጉምና የሕጎች ሕገ መንግሥታዊነት ክትትል ጉዳዮች ዳይሬክተር የነበረ፣ 2ኛ አቶ ኃ/ሚካኤል ልኬ የህግ አማካሪ እና ጠበቃ፣ 3ኛ አቶ ቃላት ባህታ በግል ስራ የሚተዳደርን ጨምሮ 7 ግለሰቦች ናቸው፡፡
በመጀመሪያ ክስ በ1ኛ፣ 2ኛ እና 3ኛ ተከሳሾች ላይ የቀረበ ሲሆን በ1996 ዓ.ም የወጣውን የወንጀል ሕግ አንቀጽ 32(1) (ሀ)፣ 33 እና የሙስና ወንጀሎችን ለመደንገግ የወጣውን አዋጅ ቁጥር 881/2007 አንቀጽ 9 (1) (ሀ) እና (2) ስር የተመለከተውን በመተላለፍ ነው፡፡
1ኛ ተከሳሽ ከ2ኛ እና 3ኛ ተከሳሾች ጋር በመመሳጠር የማይገባቸውን ጥቅም ለራሳቸው ለማግኘትና ለሌሎችም ለማስገኘት በማሰብ በኢትዮጵያና ኤርትራ መካከል ተከስቶ የነበረውን ግጭት ተከትሎ የሀገር ደህንነትን እና ህልውናን ለማስጠበቅ ሲባል ከሀገር የተሸኙ ኤርትራዊያን ንብረቶችን በጨረታ እንዲሸጥ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በሰጠው ትዕዛዝ መሰረት ከሀገር እንዲወጡ በተደረጉት ኤርትራዊ ቦሌ ክ/ከ ወረዳ 3 ስር የሚገኝ መኖርያ ቤት እና ይዞታ ለጨረታ እንዲቀርብ ተደርጎ 1ኛ የዐቃቤ ህግ ምስክር ወ/ሮ አልጋነሽ ኃይሉ የጨረታው አሸናፊ በመሆን በ1992 ዓ.ም የሽያጭ ውል በመፈፀም ቤቱን ከተረከቡ በኋላ ተከሳሾች በሀሰተኛ ደብዳቤው መነሻነት በዜግነት ኤርትራዊት የሆነችው 4ኛ ተከሳሽ ኢትዮጵያዊ ናት በሚል መደምደሚያ ላይ በመድረስ ውሉ ፈርሶ ቤቱን ወ/ሮ አልጋነሽ ኃይሉ ኤርትራዊት ለሆነችው 4ኛ ተከሳሽ ወ/ሮ ኤልሳቤት ተስፋጽዮን እንድታስረክብ በማለት የፌዴሬሽን ም/ቤት የወሰነውን ውሳኔ ድጋሚ ለምክር ቤቱ እንዳይቀርብ ለማድረግ በአካልና በስልክ በመገናኘትና በመደራደር፣ የዐቃቤ ህግ 1ኛ ምስክር ብር 400 ሚሊየን የሚገመት ቤትን እንዲያጡ አድርገዋል፡፡
በዚህም በዋና ወንጀል አድራጊነት በፈፀሙት ስልጣንን ያለአግባብ መገልገል ከባድ የሙስና ወንጀል መፈጸማቸውን ዐቃቤ ሕግ በክሱ ላይ ዘርዝሯል።
በሁተለኛ ክስ በተመሳሳይ1ኛ፣ 2ኛ፣ 5ኛ እና 6ኛ ተከሳሾች ከላይ በዝርዝር በተገለጸው የወንጀል ድርጊታቸው በህገ መንግሥት አጣሪ ጉባኤ በአብላጫው ድምጽ ትርጉም አያስፈልገውም በማለት በመወሰኑ በውሳኔው ቅር በመሰኘት የህገ መንግሥት ትርጉም ይሰጥልኝ ሲሉ ሕገ መንግሥት ትርጉም እንዲሰጣቸው ለፌዴሬሽን ም/ቤት የዕግድ እና የይግባኝ አቤቱታ በም/ቤቱ ተቀባይነት አግኝቶ ውሳኔው እንዳይቀየር በማድረግ ከፍተኛ ጥቅም ለማግኘት እና የግል ተበዳዮችን ይዞታ በማሳጣት ከፍተኛ የገንዘብ ጉዳት በማድረሳቸው 1ኛ እና 6ኛ ተከሳሾች በመንግሥት ወይም ህዝባዊ ድርጅት ሰራተኞች ብቻ በሚፈጸም የሙስና ወንጀል ውስጥ በልዩ ወንጀል አድራጊነት ተካፋይ ከሆኑት 2ኛ እና 5ኛ ተከሳሾች ጋር በዋና ወንጀል አድራጊነት ተካፋይ በመሆን በፈጸሙት የከባድ የስልጣን ያለአግባብ መገልገል ወንጀል ተከሰዋል፡፡
በሶስተኛ ክስ በ1ኛ እና 7ኛተከሳሾች 1ኛ ተከሳሽ በተጨማሪነት ለራሱም የማይገባውን 200 ሺህ ብር በማግኘቱ 1ኛ ተከሳሽ በመንግሥት ወይም ህዝባዊ ድርጅት ሰራተኞች ብቻ በሚፈጸም የሙስና ወንጀል ውስጥ በልዩ ወንጀል አድራጊነት ተካፋይ ከሆነው 7ኛ ተከሳሽ ጋር በዋና ወንጀል አድራጊነት ተካፋይ በመሆን በፈጸሙት በከባድ ስልጣንን አላግባብ መገልገል የሙስና ወንጀል የቅጣት ውሳኔ ተላልፎባቸዋል፡፡
ተከሳሾች ዛሬ የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 4ኛ የሙስና ጉዳዮች ወንጀል ችሎት በዋለዉ ችሎት 1ኛ ተከሳሽ በ6 ዓመት ከ4 ወር ጽኑ እስራት እና 3 ሺህ ብር፣ 2ኛ ተከሳሽ 2 ዓመት ከ8 ወር እና 5 ሺህ ብር፣ 3ኛ ተከሳሽ በቂ ማስረጃ ስላልተገኘበት በነጻ፣ 4ኛ ተከሳሽ 4 ዓመት ከ6 ወር፣ 5ኛ እና 6ኛ ተከሳሽ 2 ዓመት ከ8 ወር እና 1 ሺህ ብር እንዲሁም 7ኛ ተከሳሽ 7 ዓመት ከ6 ወር እና 10 ሺህ ብር እንዲቀጡ ወስኗል።
FBC
Sponsored by
Surafel
3 months ago
የሀሮማያ ሐይቅ ዳግም መወለድ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር የተፈጥሮን ጉዳት እያከመ ለመሆኑ ሕያው ማሳያ ነው፦ ተመስገን ጥሩነህ
*********************
በ1996 ዓ.ም ሙሉ በሙሉ ጠፍቶ የነበረው የሀሮማያ ሐይቅ፣ በአረንጓዴ አሻራ እና በተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ጥረት ዛሬ ወደ ቀደመ ውበትና ሥሪቱ መመለሱ ታውቋል።
ይህ የሐይቁ ዳግም መወለድ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር ከሰጣቸው ታላላቅ ፍሬዎች አንዱ ሲሆን፣ አረንጓዴ አሻራ ለኢትዮጵያ የውኃ አካላትና ለተፋሰስ ልማት ቁልፍ ኢኒሼቲቭ መሆኑን በተግባር ያረጋገጠ ስኬት ሆኗል።
ይህ የተመዘገበው ስኬት በመደመር እሳቤ ልማትን ማረጋገጥ ብቻ ሳይሆን፣ የተፈጥሮን ጫና መቋቋምና መግራት እንደሚቻል ትልቅ ማረጋገጫ መሆኑ ተገልጿል። በተጨማሪም ወደ ስፍራው በተደረገው ጉዞ በአካባቢው ለተደረገው ደማቅ አቀባበል ምስጋና መቅረቡ ታውቋል።
#haramayalake #greenlegacy #ethiopia
*********************
በ1996 ዓ.ም ሙሉ በሙሉ ጠፍቶ የነበረው የሀሮማያ ሐይቅ፣ በአረንጓዴ አሻራ እና በተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ጥረት ዛሬ ወደ ቀደመ ውበትና ሥሪቱ መመለሱ ታውቋል።
ይህ የሐይቁ ዳግም መወለድ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር ከሰጣቸው ታላላቅ ፍሬዎች አንዱ ሲሆን፣ አረንጓዴ አሻራ ለኢትዮጵያ የውኃ አካላትና ለተፋሰስ ልማት ቁልፍ ኢኒሼቲቭ መሆኑን በተግባር ያረጋገጠ ስኬት ሆኗል።
ይህ የተመዘገበው ስኬት በመደመር እሳቤ ልማትን ማረጋገጥ ብቻ ሳይሆን፣ የተፈጥሮን ጫና መቋቋምና መግራት እንደሚቻል ትልቅ ማረጋገጫ መሆኑ ተገልጿል። በተጨማሪም ወደ ስፍራው በተደረገው ጉዞ በአካባቢው ለተደረገው ደማቅ አቀባበል ምስጋና መቅረቡ ታውቋል።
#haramayalake #greenlegacy #ethiopia
3 months ago
የፀጉር መጠን በአንድ ሰው የማሰብ ችሎታ (intelligence) ላይ ለምን ተጽዕኖ ያሳድራል?
አንድ አሜሪካዊ የስነ-ልቦና ባለሙያ በዚህ ጥያቄ ላይ ጥናት አድርገው የሰውነት ፀጉር መጠን የማሰብ ችሎታ ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድር ደርሰውበታል፦ የሰውነት ፀጉር በበዛ ቁጥር የበለጠ ብልህ ይሆናሉ።
እ.ኤ.አ. በ1996 ዶክተር አይካራኩዲ አሊያስ (Dr. Aikarakudi Alias) የደረት ፀጉር በሀኪሞች እና ከፍተኛ ትምህርት ባላቸው ሰዎች መካከል በብዛት እንደሚታይ ገልጸው ነበር።
seledadotio
seledadotio
አንድ አሜሪካዊ የስነ-ልቦና ባለሙያ በዚህ ጥያቄ ላይ ጥናት አድርገው የሰውነት ፀጉር መጠን የማሰብ ችሎታ ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድር ደርሰውበታል፦ የሰውነት ፀጉር በበዛ ቁጥር የበለጠ ብልህ ይሆናሉ።
እ.ኤ.አ. በ1996 ዶክተር አይካራኩዲ አሊያስ (Dr. Aikarakudi Alias) የደረት ፀጉር በሀኪሞች እና ከፍተኛ ትምህርት ባላቸው ሰዎች መካከል በብዛት እንደሚታይ ገልጸው ነበር።
seledadotio
seledadotio
4 months ago
በ600 ሚሊዮን ብር ማጭበርበር የተከሰሰው የፊንቴክ ኢንቨስትመንት ሥራ አስኪያጅ ጉዳይ
#fastmereja I በኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ሽያጭ ስም "ዘመናዊ ታክሲዎችን በዱቤ እናቀርባለን" በሚሉ አማላይ ማስታወቂያዎች ከ600 ሚሊዮን ብር በላይ ከዜጎች የሰበሰበው የፊንቴክ ኢንቨስትመንት ሥራ አስኪያጅ ዳንኤል ዮሐንስ ክስ ተመሰረተበት።
ተከሳሹ በማኅበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪዎችን በመጠቀምና አሳሳች መረጃዎችን በማሰራጨት በፈጸመው መጠነ ሰፊ ማጭበርበር በፌዴራል ዐቃቤ ሕግ 19 ተደራራቢ ክሶች ቀርበውበታል።
የፌዴራል ዐቃቤ ሕግ ለፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 2ኛ ልዩ ልዩ ወንጀል ችሎት ባቀረበው ዝርዝር መሠረት፣ ግለሰቡ ወንጀሉን የፈጸመው በንግድና በሕጋዊ ሽፋን በተደራጀ "የነጭ ኮሌታ ሳይበር ማጭበርበር" ስልት መሆኑ ተመልክቷል።
ተከሳሹ በ2013 ዓ.ም "ሄሎ ታክሲ" እና "ሄሎ መኪና" የተባሉ ድርጅቶችን በማቋቋም፣ የትራንስፖርት ችግርን ለመፍታት ዘመናዊ መኪናዎችን በዱቤ እንደሚያቀርብ በማብሰር ከ5 ሺህ በላይ ዜጎችን መዝግቧል። ለእያንዳንዱ ምዝገባና ቅድመ ክፍያ እስከ 247,500 ብር ካሰባሰበ በኋላ ድርጅቱን ዘግቶ መሰወሩ ተገልጿል።
ዳንኤል ዮሐንስ ቀደም ሲል በዓለም ዋንጫ ስም ማጭበርበር ፈጽሞ በኢንተርፖል ከተያዘው ግርማይ ገብረሚካኤል (አስካል) ከተባለ ግብረ-አበሩ ጋር በመሆን፣ በ2016 ዓ.ም "ፊንቴክ ኢንቨስትመንት" የተባለ ድርጅት በ7 ሚሊዮን ብር ካፒታል አቋቁሟል።
ድርጅቱ የቻይናውን "ቢዋይዲ" (BYD) የኤሌክትሪክ መኪኖች በዱቤ እንደሚያቀርብ በማስመሰል፣ ታዋቂ አርቲስቶችንና ቲክቶከሮችን በመጠቀም ሰፊ ማስታወቂያ አስነግሯል። በመስቀል አደባባይና በስካይ ላይት ሆቴል መኪናዎችን እንዳስረከቡ የሚያሳዩ የሐሰት ምስሎችን በማሰራጨት የሕዝብን እምነት ማግኘታቸው ተረጋግጧል።
ተከሳሹ ከ1,430 በላይ ግለሰቦችን በመመዝገብ ከእያንዳንዱ ሰው ከ950 ሺህ እስከ 1.86 ሚሊዮን ብር የሰበሰበ ቢሆንም፣ ለጥቂት የጥቅም ተጋሪዎቹ ብቻ መኪና በመስጠት የተቀሩትን ሳይበድል ቀርቷል። በማስታወቂያው ላይ ግን 520 መኪናዎችን እንዳከፋፈለ በመግለጽ የሐሰት ሪፖርት ሲያቀርብ እንደነበር ዐቃቤ ሕግ አመልክቷል።
ተከሳሹ በ1996 ዓ.ም የወጣውን የወንጀል ሕግ እና የኮምፒውተር ወንጀል አዋጅን በመተላለፍ ክስ የተመሰረተበት ሲሆን፣ ጉዳዩ በፍርድ ቤት መታየት ጀምሯል።
መጋቢት 18 ቀን 2018 ዓ.ም
#fastmereja I በኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ሽያጭ ስም "ዘመናዊ ታክሲዎችን በዱቤ እናቀርባለን" በሚሉ አማላይ ማስታወቂያዎች ከ600 ሚሊዮን ብር በላይ ከዜጎች የሰበሰበው የፊንቴክ ኢንቨስትመንት ሥራ አስኪያጅ ዳንኤል ዮሐንስ ክስ ተመሰረተበት።
ተከሳሹ በማኅበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪዎችን በመጠቀምና አሳሳች መረጃዎችን በማሰራጨት በፈጸመው መጠነ ሰፊ ማጭበርበር በፌዴራል ዐቃቤ ሕግ 19 ተደራራቢ ክሶች ቀርበውበታል።
የፌዴራል ዐቃቤ ሕግ ለፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 2ኛ ልዩ ልዩ ወንጀል ችሎት ባቀረበው ዝርዝር መሠረት፣ ግለሰቡ ወንጀሉን የፈጸመው በንግድና በሕጋዊ ሽፋን በተደራጀ "የነጭ ኮሌታ ሳይበር ማጭበርበር" ስልት መሆኑ ተመልክቷል።
ተከሳሹ በ2013 ዓ.ም "ሄሎ ታክሲ" እና "ሄሎ መኪና" የተባሉ ድርጅቶችን በማቋቋም፣ የትራንስፖርት ችግርን ለመፍታት ዘመናዊ መኪናዎችን በዱቤ እንደሚያቀርብ በማብሰር ከ5 ሺህ በላይ ዜጎችን መዝግቧል። ለእያንዳንዱ ምዝገባና ቅድመ ክፍያ እስከ 247,500 ብር ካሰባሰበ በኋላ ድርጅቱን ዘግቶ መሰወሩ ተገልጿል።
ዳንኤል ዮሐንስ ቀደም ሲል በዓለም ዋንጫ ስም ማጭበርበር ፈጽሞ በኢንተርፖል ከተያዘው ግርማይ ገብረሚካኤል (አስካል) ከተባለ ግብረ-አበሩ ጋር በመሆን፣ በ2016 ዓ.ም "ፊንቴክ ኢንቨስትመንት" የተባለ ድርጅት በ7 ሚሊዮን ብር ካፒታል አቋቁሟል።
ድርጅቱ የቻይናውን "ቢዋይዲ" (BYD) የኤሌክትሪክ መኪኖች በዱቤ እንደሚያቀርብ በማስመሰል፣ ታዋቂ አርቲስቶችንና ቲክቶከሮችን በመጠቀም ሰፊ ማስታወቂያ አስነግሯል። በመስቀል አደባባይና በስካይ ላይት ሆቴል መኪናዎችን እንዳስረከቡ የሚያሳዩ የሐሰት ምስሎችን በማሰራጨት የሕዝብን እምነት ማግኘታቸው ተረጋግጧል።
ተከሳሹ ከ1,430 በላይ ግለሰቦችን በመመዝገብ ከእያንዳንዱ ሰው ከ950 ሺህ እስከ 1.86 ሚሊዮን ብር የሰበሰበ ቢሆንም፣ ለጥቂት የጥቅም ተጋሪዎቹ ብቻ መኪና በመስጠት የተቀሩትን ሳይበድል ቀርቷል። በማስታወቂያው ላይ ግን 520 መኪናዎችን እንዳከፋፈለ በመግለጽ የሐሰት ሪፖርት ሲያቀርብ እንደነበር ዐቃቤ ሕግ አመልክቷል።
ተከሳሹ በ1996 ዓ.ም የወጣውን የወንጀል ሕግ እና የኮምፒውተር ወንጀል አዋጅን በመተላለፍ ክስ የተመሰረተበት ሲሆን፣ ጉዳዩ በፍርድ ቤት መታየት ጀምሯል።
መጋቢት 18 ቀን 2018 ዓ.ም
4 months ago
የፊንቴክ ኢንቨስትመንት ስራ አስኪያጅ ተከሰሰ
ተፅዕኖ ፈጣሪዎችን ማስታወቂያ በማስነገር የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች እናስረክባለን በማለት ከ600 ሚሊየን ብር በላይ ከተበዳዮች የሰበሰበው ፊንቴክ ኢንቨስትመንት ስራ አስኪያጅ የሆነው ዳንኤል ዮሐንስ ክስ ተመስርቶበታል።
ተከሳሽ በ1996 ዓ.ም የወጣውን የወንጀል ህግ አንቀፅ 32 ቁጥር 1 ሀ እና ለ እንዲሁም አንቀጽ 35፣ 38 እንዲሁም የኮምፒውተር ወንጀል አዋጅ ቁጥር 958/2008 አንቀፅ 10 ቁጥር 1 ስር የተደነገገውን በመተላለፍ ነው ክስ የተመሰረተበት።
ተከሳሽ ለጊዜው ካልተያዙ ተጠርጣሪዎች ጋር በመሆን ኮምፒውተርን ወይም የኮምፒውተር ስርዓትን በመጠቀም አሳሳች ዳታ በማሰራጨት፣ የራሳቸውን በመሰወር ወይም መግለፅ የሚገባቸውን ነገር በመደበቅ ወይም የሌላውን ሰው የተሳሳተ እምነት በመጠቀም፣ ሌላውን ሰው አታልለው የተበዳይን ጥቅም የሚጎዳ ድርጊት እንዲፈፀም ለማድረግ በማሰብ ወንጀል ለመፈፀም ባደረጉት ስምምነት መሰረት የወንጀል ድርጊት መፈጸማቸውን ዐቃቤ ሕግ በክስ ዝርዝሩ ላይ አመልክቷል።
በዚህም ተከሳሽ በ2013 ዓ.ም በመጀመሪያ ሄሎ ታክሲ እና ሄሎ መኪና የተባሉትን ድርጅቶች ካቋቋመ በኋላ ድርጅቱ የታክሲ ሥራን ለማዘመን ዘመናዊ መኪኖችን ከሀገር ውስጥ አቅራቢዎች እና ከውጭ ሀገር በማስመጣት እንዲሁም በመገጣጠም በመንገድ እና ትራንስፖርት ባለስልጣን (ሚኒስቴር) ባወጣው መመሪያ መሰረት አሁን ያለውን የትራንስፖርት ችግር ለመፍታት ለታክሲ ፈላጊዎች ዘመናዊ ታክሲ በዱቤ እናቀርባለን በሚል አሳሳች መረጃዎችን አሰራጭተዋል ብሏል በክሱ።
በመረጃው መሰረት ከ5 ሺህ በላይ የሚሆኑ ግለሰቦች ተከሳሽ እና የተከሳሽ ድርጅት በተለያዩ በመንግሥት፣ በግል እና ማህበራዊ ሚዲያዎች የተሰራጨውን ማስታወቂያዎችን በመመልከት ወደ ድርጅቱ የሄዱ የግል ተበዳዮች በዱቤ ሰርታችሁ ትርፋማ የምትሆኑበትን ታክሲ ገንዘቡን በከፈላችሁት በ3 ወር ውስጥ እናስረክባቸዋለን በማለት 60 ሺህ ብር ለመመዝገቢያ፣ ከመኪናው ጠቅላላ ዋጋ 25 በመቶ ወይም 247 ሺህ 500 ብር በድርጅቱ አካውንት ላይ ገቢ እንዲያደርጉ በማድረግ የግል ተበዳዮች እምነት እንዲጥሉባችው ለማድረግ እና በረቀቀ መንገድ ወንጀሉን ለመፈፀም እንዲያመቻቸው ውል በማርቀቅ እና በድርጅቱ በተረቀቀው ውል ላይ እንዲፈርሙ ማድረግ የሚል በክሱ ላይ ተገልጿል።
ከዚህ በተጨማሪ የመኪኖቻችውን ሻንሲ እና ሞተር ቁጥር ስለመጣ ፈርማችሁ ውሰዱ በማለት ከሄሎ ታክሲ ከሚል ድርጅት የሞተር እና ሻንሲ ቁጥር ላይ ፈርመው እንዲወስዱ ካደረገ በኋላ ከ600 ሚሊየን ብር በላይ ተቀብሎ መኪናውን ሳያስረክብ ድርጅቱን ዘግቶ መሰወር በክሱ ላይ ከተነሱ ጉዳዮች መካከል ነው።
እንዲሁም ተከሳሽ ግርማይ ገ/ሚካኤል ከተባለው (አስካል የተባለውን ድርጅት በማቋቋም በድርጅቱ ስም በ2002 ዓ.ም በተካሄደው የዓለም ዋንጫ ጨዋታ ላይ በርካታ ኢትዮጵያውያን እንዲታደሙ ወደ ደቡብ አፍሪካ እልካቸዋለሁ በማለት ብር በመቀበል ተሰውሮ በኢንተርፖል የተያዘ) ለጊዜው ካልተያዘው ግብረ-አበር ጋር በመሆን ከዚህ በፊት ከላይ የፈፀሙትን እና ከላይ የተገለፀውን ወንጀል በሰፊው ለመፈፀም በሕጋዊ፣ በንግድ እና ውል ሽፋን ስም በተለምዶ የነጭ ኮሌታ ሳይበር አታላዮች የሚፈፅሙት ወንጀል ለመፈፀም እንዲያመቻቸው ፊንቴክ ኢንቨስትመንት ኃ/የተ/የግ/ማህበር የተባለውን ድርጅት በተሽካርከሪዎች አስመጪነት፣ በተሽካርከሪዎች መለዋወጫ፤ መቆጣጠሪያ መሳሪያዎችን እና ጌጣጌጦች አስመጪነት እና የተሽካርከሪዎች ከአካላት እና ተሳቢዎች አስመጪነት 7 ሚሊየን ብር ካፒታል በማቋቋም ከአዲስ አበባ ንግድ እና ኢንዱስትሪ ቢሮ በግንቦት 3 ቀን 2016 ዓ.ም የንግድ ፍቃድ ያወጡ መሆኑ፤ ድርጅታችን የኤሌክትሪክ መኪኖችን በቀጥታ ከቻይና ቢዋይዲ ኩባንያ በማስመጣት በጠቅላላ ዋጋ 1 ሚሊየን 900 ሺህ ብር ለደንበኞች በ50 በመቶ ወይም 950 ሺህ ብር ቅድሚያ ክፍያ እና ቀሪው የ50 በመቶ በዱቤ ሽያጭ ወደ ሀገር ውስጥ በማስገባት ለደንበኞች በማስረከብ ላይ ይገኛል፤ ማንኛውም ተቋም ያላደረገውን ቀሪውን 950 ሺህ ብር 50 በመቶ ያለወለድ በ5 ዓመት ውስጥ ከፍለው የሚጨርሱበት አሰራር በመዘርጋት የመኪና ባለቤት ሊያደርጋችሁ ተዘጋጅቷል፤ ስለዚህ ተመዝግበው በ3 ወር ውስጥ የመኪና ባለቤት ይሁኑ የሚሉ ማስታወቂያዎችን በማሰራት።
በኦሮሚያ ባህል ማዕከል፣ በስካይ ላይት ሆቴል፣ በመስቀል አደባባይ እና በወዳጅነት አደባባይ እንዳስረከቡ የሚያሳይ ቪድዮ እና ፎቶ በመልቀቅ እና በማሳየት እስካሁን ከ450 በላይ መኪኖችን ለተመዝጋቢዎች ያስረከበ መሆኑን፤ አሁንም ለደንበኞቻችን ለማስረከብ ወደ 400 መኪኖችን ወደ ሀገር ውስጥ እያጓጓዝን እናገኛለን፤ ኑ እና ከፍለው ቀሪውን 950 ሺህ ብር ያለወለድ እየከፈሉ የመኪና ባለቤት ይሁኑ፤ ለመኪናው ለ5 ዓመት ዋስትና እንሰጣለን፤ ድርጅታችን ከፀሐይ ኢንሹራንስ ጋር የኢንሹራንስ ውል ገብቷል፣ ከባንክ ጋር አገናኝተናል” በማለት የተለያዩ ማስታወቂያዎችን በታዋቂ ግለሰቦች፣ ታዋቂ አርቲስቶችን፣ ቲክቶከሮችን፣ የመንግሥት እና የግል ሚዲያዎችን እንዲሁም የራሳቸውን ሚዲያ ጨምሮ የተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያዎችን በመጠቀም ማስታወቂያውን በማሰራጨት በርካታ ሰዎች በተከሳሽ እና በተከሳሽ ድርጅት የተሰራጨውን ትርፋማ የምትሆኑበትን ዘመናዊ የኤሌክትሪክ መኪና እናቀርባለን የሚል አማላይ እና አሳሳች ማስታወቂያዎችን በመመልከት በርካታ ግለሰቦች ወደ ድርጅቱ ሄደው በመመዝገብ ቅድመ ክፍያ 950 ሺህ ብር ከከፈሉ በኋላ በማስታወቂያ ላይ ከተነገረው ገንዘብ 950 ሺህ ብር በተጨማሪ (ተጨማሪ እሴት ታክሲ) በሚል 285 ሺህ ብር እና ለቦሎ እና ለታርጋ ተብሎ ከ130 ሺህ ብር እንዲከፍሉ አድርገዋል ሲል ዐቃቤ ሕግ በክሱ ዝርዝር ላይ አመልክቷል።
በአጠቃላይ 1 ሚሊየን 365 ሺህ ብር በማስከፈል በ3 ወር ውስጥ መኪና እናስረክባለን በማለት በተከሳሽ እና በተከሳሽ ድርጅት በተረቀቀው ውል ላይ እንዲፈርሙ በማድረግ እንዲሁም በ3 ወር ውስጥ መኪና አስረክባቸዋለሁ በማለት ከ1 ሺህ 430 በላይ ግለሰቦችን በመመዝገብ ከእያንዳንዱ ተመዝጋቢ ከብር 950 ሺህ እስከ 1 ነጥብ 86 ሚሊየን ብር በላይ ሰብስበው 100 መኪኖችን ለራሱ፣ ግብረ-አበሩ እና የጥቅም ተጋሪ ለሆኑ ግለሰቦች ብቻ አስረክቦ ሳለ በሚዲያዎች ከ520 በላይ መኪኖችን አስረክበናል በማለት አሳሳች መረጃዎችን በመናገር ግለሰቦች ቀርበው እንዲመዘገቡ እና ገንዘብ እንዲከፍሉ ሲያደርግ ነበረ በሚል 19 ተደራራቢ ክሶች ተመስርተውበታል።
የክስ መዝገቡን የተመለከተው የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 2ኛ ልዩ ልዩ ወንጀል ችሎት ነው።
FBC
ተፅዕኖ ፈጣሪዎችን ማስታወቂያ በማስነገር የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች እናስረክባለን በማለት ከ600 ሚሊየን ብር በላይ ከተበዳዮች የሰበሰበው ፊንቴክ ኢንቨስትመንት ስራ አስኪያጅ የሆነው ዳንኤል ዮሐንስ ክስ ተመስርቶበታል።
ተከሳሽ በ1996 ዓ.ም የወጣውን የወንጀል ህግ አንቀፅ 32 ቁጥር 1 ሀ እና ለ እንዲሁም አንቀጽ 35፣ 38 እንዲሁም የኮምፒውተር ወንጀል አዋጅ ቁጥር 958/2008 አንቀፅ 10 ቁጥር 1 ስር የተደነገገውን በመተላለፍ ነው ክስ የተመሰረተበት።
ተከሳሽ ለጊዜው ካልተያዙ ተጠርጣሪዎች ጋር በመሆን ኮምፒውተርን ወይም የኮምፒውተር ስርዓትን በመጠቀም አሳሳች ዳታ በማሰራጨት፣ የራሳቸውን በመሰወር ወይም መግለፅ የሚገባቸውን ነገር በመደበቅ ወይም የሌላውን ሰው የተሳሳተ እምነት በመጠቀም፣ ሌላውን ሰው አታልለው የተበዳይን ጥቅም የሚጎዳ ድርጊት እንዲፈፀም ለማድረግ በማሰብ ወንጀል ለመፈፀም ባደረጉት ስምምነት መሰረት የወንጀል ድርጊት መፈጸማቸውን ዐቃቤ ሕግ በክስ ዝርዝሩ ላይ አመልክቷል።
በዚህም ተከሳሽ በ2013 ዓ.ም በመጀመሪያ ሄሎ ታክሲ እና ሄሎ መኪና የተባሉትን ድርጅቶች ካቋቋመ በኋላ ድርጅቱ የታክሲ ሥራን ለማዘመን ዘመናዊ መኪኖችን ከሀገር ውስጥ አቅራቢዎች እና ከውጭ ሀገር በማስመጣት እንዲሁም በመገጣጠም በመንገድ እና ትራንስፖርት ባለስልጣን (ሚኒስቴር) ባወጣው መመሪያ መሰረት አሁን ያለውን የትራንስፖርት ችግር ለመፍታት ለታክሲ ፈላጊዎች ዘመናዊ ታክሲ በዱቤ እናቀርባለን በሚል አሳሳች መረጃዎችን አሰራጭተዋል ብሏል በክሱ።
በመረጃው መሰረት ከ5 ሺህ በላይ የሚሆኑ ግለሰቦች ተከሳሽ እና የተከሳሽ ድርጅት በተለያዩ በመንግሥት፣ በግል እና ማህበራዊ ሚዲያዎች የተሰራጨውን ማስታወቂያዎችን በመመልከት ወደ ድርጅቱ የሄዱ የግል ተበዳዮች በዱቤ ሰርታችሁ ትርፋማ የምትሆኑበትን ታክሲ ገንዘቡን በከፈላችሁት በ3 ወር ውስጥ እናስረክባቸዋለን በማለት 60 ሺህ ብር ለመመዝገቢያ፣ ከመኪናው ጠቅላላ ዋጋ 25 በመቶ ወይም 247 ሺህ 500 ብር በድርጅቱ አካውንት ላይ ገቢ እንዲያደርጉ በማድረግ የግል ተበዳዮች እምነት እንዲጥሉባችው ለማድረግ እና በረቀቀ መንገድ ወንጀሉን ለመፈፀም እንዲያመቻቸው ውል በማርቀቅ እና በድርጅቱ በተረቀቀው ውል ላይ እንዲፈርሙ ማድረግ የሚል በክሱ ላይ ተገልጿል።
ከዚህ በተጨማሪ የመኪኖቻችውን ሻንሲ እና ሞተር ቁጥር ስለመጣ ፈርማችሁ ውሰዱ በማለት ከሄሎ ታክሲ ከሚል ድርጅት የሞተር እና ሻንሲ ቁጥር ላይ ፈርመው እንዲወስዱ ካደረገ በኋላ ከ600 ሚሊየን ብር በላይ ተቀብሎ መኪናውን ሳያስረክብ ድርጅቱን ዘግቶ መሰወር በክሱ ላይ ከተነሱ ጉዳዮች መካከል ነው።
እንዲሁም ተከሳሽ ግርማይ ገ/ሚካኤል ከተባለው (አስካል የተባለውን ድርጅት በማቋቋም በድርጅቱ ስም በ2002 ዓ.ም በተካሄደው የዓለም ዋንጫ ጨዋታ ላይ በርካታ ኢትዮጵያውያን እንዲታደሙ ወደ ደቡብ አፍሪካ እልካቸዋለሁ በማለት ብር በመቀበል ተሰውሮ በኢንተርፖል የተያዘ) ለጊዜው ካልተያዘው ግብረ-አበር ጋር በመሆን ከዚህ በፊት ከላይ የፈፀሙትን እና ከላይ የተገለፀውን ወንጀል በሰፊው ለመፈፀም በሕጋዊ፣ በንግድ እና ውል ሽፋን ስም በተለምዶ የነጭ ኮሌታ ሳይበር አታላዮች የሚፈፅሙት ወንጀል ለመፈፀም እንዲያመቻቸው ፊንቴክ ኢንቨስትመንት ኃ/የተ/የግ/ማህበር የተባለውን ድርጅት በተሽካርከሪዎች አስመጪነት፣ በተሽካርከሪዎች መለዋወጫ፤ መቆጣጠሪያ መሳሪያዎችን እና ጌጣጌጦች አስመጪነት እና የተሽካርከሪዎች ከአካላት እና ተሳቢዎች አስመጪነት 7 ሚሊየን ብር ካፒታል በማቋቋም ከአዲስ አበባ ንግድ እና ኢንዱስትሪ ቢሮ በግንቦት 3 ቀን 2016 ዓ.ም የንግድ ፍቃድ ያወጡ መሆኑ፤ ድርጅታችን የኤሌክትሪክ መኪኖችን በቀጥታ ከቻይና ቢዋይዲ ኩባንያ በማስመጣት በጠቅላላ ዋጋ 1 ሚሊየን 900 ሺህ ብር ለደንበኞች በ50 በመቶ ወይም 950 ሺህ ብር ቅድሚያ ክፍያ እና ቀሪው የ50 በመቶ በዱቤ ሽያጭ ወደ ሀገር ውስጥ በማስገባት ለደንበኞች በማስረከብ ላይ ይገኛል፤ ማንኛውም ተቋም ያላደረገውን ቀሪውን 950 ሺህ ብር 50 በመቶ ያለወለድ በ5 ዓመት ውስጥ ከፍለው የሚጨርሱበት አሰራር በመዘርጋት የመኪና ባለቤት ሊያደርጋችሁ ተዘጋጅቷል፤ ስለዚህ ተመዝግበው በ3 ወር ውስጥ የመኪና ባለቤት ይሁኑ የሚሉ ማስታወቂያዎችን በማሰራት።
በኦሮሚያ ባህል ማዕከል፣ በስካይ ላይት ሆቴል፣ በመስቀል አደባባይ እና በወዳጅነት አደባባይ እንዳስረከቡ የሚያሳይ ቪድዮ እና ፎቶ በመልቀቅ እና በማሳየት እስካሁን ከ450 በላይ መኪኖችን ለተመዝጋቢዎች ያስረከበ መሆኑን፤ አሁንም ለደንበኞቻችን ለማስረከብ ወደ 400 መኪኖችን ወደ ሀገር ውስጥ እያጓጓዝን እናገኛለን፤ ኑ እና ከፍለው ቀሪውን 950 ሺህ ብር ያለወለድ እየከፈሉ የመኪና ባለቤት ይሁኑ፤ ለመኪናው ለ5 ዓመት ዋስትና እንሰጣለን፤ ድርጅታችን ከፀሐይ ኢንሹራንስ ጋር የኢንሹራንስ ውል ገብቷል፣ ከባንክ ጋር አገናኝተናል” በማለት የተለያዩ ማስታወቂያዎችን በታዋቂ ግለሰቦች፣ ታዋቂ አርቲስቶችን፣ ቲክቶከሮችን፣ የመንግሥት እና የግል ሚዲያዎችን እንዲሁም የራሳቸውን ሚዲያ ጨምሮ የተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያዎችን በመጠቀም ማስታወቂያውን በማሰራጨት በርካታ ሰዎች በተከሳሽ እና በተከሳሽ ድርጅት የተሰራጨውን ትርፋማ የምትሆኑበትን ዘመናዊ የኤሌክትሪክ መኪና እናቀርባለን የሚል አማላይ እና አሳሳች ማስታወቂያዎችን በመመልከት በርካታ ግለሰቦች ወደ ድርጅቱ ሄደው በመመዝገብ ቅድመ ክፍያ 950 ሺህ ብር ከከፈሉ በኋላ በማስታወቂያ ላይ ከተነገረው ገንዘብ 950 ሺህ ብር በተጨማሪ (ተጨማሪ እሴት ታክሲ) በሚል 285 ሺህ ብር እና ለቦሎ እና ለታርጋ ተብሎ ከ130 ሺህ ብር እንዲከፍሉ አድርገዋል ሲል ዐቃቤ ሕግ በክሱ ዝርዝር ላይ አመልክቷል።
በአጠቃላይ 1 ሚሊየን 365 ሺህ ብር በማስከፈል በ3 ወር ውስጥ መኪና እናስረክባለን በማለት በተከሳሽ እና በተከሳሽ ድርጅት በተረቀቀው ውል ላይ እንዲፈርሙ በማድረግ እንዲሁም በ3 ወር ውስጥ መኪና አስረክባቸዋለሁ በማለት ከ1 ሺህ 430 በላይ ግለሰቦችን በመመዝገብ ከእያንዳንዱ ተመዝጋቢ ከብር 950 ሺህ እስከ 1 ነጥብ 86 ሚሊየን ብር በላይ ሰብስበው 100 መኪኖችን ለራሱ፣ ግብረ-አበሩ እና የጥቅም ተጋሪ ለሆኑ ግለሰቦች ብቻ አስረክቦ ሳለ በሚዲያዎች ከ520 በላይ መኪኖችን አስረክበናል በማለት አሳሳች መረጃዎችን በመናገር ግለሰቦች ቀርበው እንዲመዘገቡ እና ገንዘብ እንዲከፍሉ ሲያደርግ ነበረ በሚል 19 ተደራራቢ ክሶች ተመስርተውበታል።
የክስ መዝገቡን የተመለከተው የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 2ኛ ልዩ ልዩ ወንጀል ችሎት ነው።
FBC
5 months ago
ፖላንድ አሁን በዓለም ላይ ካሉ 20 ግዙፍ ኢኮኖሚዎች ተርታ ተሰልፋለች፦ ይህ እንዴት ሊሆን ቻለ?
በ1989 የኮሚኒዝም ውድቀትን ተከትሎ የፖላንድ ኢኮኖሚ አስገራሚ ለውጥ አሳይቷል። በአንድ ወቅት ደካማና ያልተረጋጋ የነበረው ኢኮኖሚዋ፣ ዛሬ በአውሮፓ ውስጥ ስኬታማ ከሚባሉት አንዱ ሆኗል።
ከአንድ ትውልድ በፊት በፖላንድ ስኳር እና ዱቄት የሚገዙት በኩፖን ነበር፤ ዜጎቿም ከምዕራብ ጀርመናውያን ጋር ሲነጻጸር የአስረኛ እጅ ያህል ብቻ ነበር የሚያገኙት። ዛሬ ግን የሀገሪቱ ኢኮኖሚ ስዊዘርላንድን በመቅደም፣ ከቢሊዮን ዶላር በላይ ዓመታዊ የሀገር ውስጥ ምርት (GDP) በማስመዝገብ በዓለም 20ኛው ግዙፍ ኢኮኖሚ ለመሆን በቅቷል።
ይህ ከ1989-90 የኮሚኒዝም ፍርስራሽ ተነስተው ወደ አውሮፓ የእድገት ሻምፒዮንነት የተደረገ ታሪካዊ ዝላይ ነው - ይህም ለተራው ህዝብ ብልጽግናን እንዴት ማምጣት እንደሚቻል ትምህርት የሚሰጥ መሆኑን ኢኮኖሚስቶች ይናገራሉ።
የዶናልድ ትራምፕ አስተዳደርም ይህ ዕውቅና ሊሰጠው ይገባል በሚል ፖላንድ በቀጣይ ዓመት በሚካሄደው የቡድን 20 ጉባኤ ላይ እንድትጋበዝ ፍላጎት አለው።
ይህ ለውጥ እንደ ጆአና ኮዋልስካ ባሉ ሰዎች ሕይወት ውስጥ ይንጸባረቃል። በበርሊን እና በዋርሶ መካከል በምትገኘው ፖዝናን ከተማ ውስጥ መሃንዲስ የሆነችው ጆአና፣ በአሜሪካ ለአምስት ዓመታት ከቆየች በኋላ ወደ ሀገሯ ተመልሳለች።
"ወደ ፖላንድ ከተመለስኩ በኋላ የሚናፍቀኝ ነገር እንዳለ ብዙ ጊዜ እጠየቃለሁ፣ እውነቱን ለመናገር ግን ተቃራኒው ነው የሚሰማኝ" ትላለች። "በብዙ ዘርፎች ከአሜሪካ ቀድመን እንገኛለን።"
ኮዋልስካ በፖዝናን የሱፐር ኮምፒውቲንግ እና ኔትወርክ ማእከል ውስጥ ትሰራለች። ማእከሉ በፖላንድ የመጀመሪያውን አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ (AI) ፋብሪካ እያለማ ሲሆን፣ በአውሮፓ ህብረት ከሚደገፉ አስር የኳንተም ኮምፒውተሮች አንዱ ጋርም እያገናኘው ይገኛል።
በፖዝናን ቴክኒካል ዩኒቨርሲቲ ከተመረቀች በኋላ በአሜሪካ ማይክሮሶፍት ውስጥ የሰራች ቢሆንም፣ "የተልዕኮ ስሜት" ይጎድላት እንደነበር ትናገራለች። "በተለይ በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ረገድ ቴክኖሎጂው በፖላንድ በሚገርም ፍጥነት እያደገ ነው፤ ለዚህም ነው መመለሱ በጣም የሳበኝ" ትላለች።
ከድህነት መውጣት
ለቡድን 20 ጉባኤ የቀረበው ግብዣ ትልቅ ትርጉም ያለው ቢሆንም፣ እስካሁን በንግድ ቡድኑ ውስጥ እንግዳ ሀገር ሙሉ አባል የሆነችበት አጋጣሚ የለም። ሆኖም ግን አሃዞቹ የራሳቸውን ታሪክ ይናገራሉ፦ በ35 ዓመታት ውስጥ የፖላንድ የነፍስ ወከፍ ገቢ በ2025 ወደ 55,340 ዶላር አድጓል፣ ይህም የአውሮፓ ህብረት አማካይ 85% ነው።
በ1990 ከነበረበት 6,730 ዶላር ሲነጻጸር ግዙፍ ዝላይ ሲሆን፣ አሁን በዓለም አቀፍ የገንዘብ ድርጅት (IMF) መረጃ መሠረት ከጃፓን (52,039 ዶላር) ጋር እኩል ደረጃ ላይ ትገኛለች።
ፖላንድ እ.ኤ.አ. በ2004 የአውሮፓ ህብረትን ከተቀላቀለች በኋላ፣ ኢኮኖሚዋ በአማካይ በዓመት 3.8% አድጓል፤ ይህም ከአውሮፓ አማካይ 1.8% በእጥፍ ይበልጣል።
እንደ ማርሲን ፒዮንትኮቭስኪ ገለጻ፣ ለዚህ ስኬት ቁልፉ አንድ ምክንያት ብቻ አይደለም። ዋነኞቹ ምክንያቶች የሚከተሉት ናቸው፦
ጠንካራ ተቋማት፦ ገለልተኛ የዳኝነት አካል፣ ፍትሃዊ ውድድርን የሚያረጋግጥ የፀረ-ሞኖፖሊ ተቋም እና የባንክ ቀውስን የሚከላከሉ ጠንካራ ደንቦች።
ሙስናን መከላከል፦ ለተቋማቱ ጥንካሬ ምስጋና ይግባውና እንደሌሎች የቀድሞ ኮሚኒስት ሀገራት ኢኮኖሚው በሙስና እና በባለሀብቶች አልተመዘበረም።
የአውሮፓ ህብረት ድጋፍ፦ ከህብረቱ የተገኘው በቢሊዮን የሚቆጠር ዩሮ እርዳታ እና የጋራ ገበያ ተጠቃሚነት።
ፖለቲካዊ ስምምነት፦ የርዕዮተ ዓለም ልዩነት ሳይገድባቸው፣ ሁሉም የፖለቲካ ኃይሎች ወደ አውሮፓ ህብረት የመግባት የረጅም ጊዜ ግብ ላይ ተስማምተው መቆየታቸው።
"ፖላንዳውያን ወዴት እንደሚሄዱ ያውቁ ነበር" ይላሉ ፒዮንትኮቭስኪ። ምዕራባውያን ለ500 ዓመታት ያዳበሩትን የተቋማት አሰራር እና ህጎችን ፖላንድ በአጭር ጊዜ ወስዳ ተግባራዊ አድርጋለች።
የሶላሪስ ኩባንያ ስኬት
በ1996 በፖዝናን የተመሰረተው የሶላሪስ ኩባንያ፣ ዛሬ 15% የገበያ ድርሻ በመያዝ በአውሮፓ ግንባር ቀደም የኤሌክትሪክ አውቶቡስ አምራች ነው።
ይህ ኩባንያ የፖላንድን የስራ ፈጣሪነት እና የፈጠራ ብቃት ማሳያ ነው። እ.ኤ.አ. በ2011 ገና በአውሮፓ የኤሌክትሪክ ቴክኖሎጂ ባልተለመደበት ወቅት ምርቱን በመጀመሩ የቴክኖሎጂ መሪ መሆን ችሏል።
ፈታኝ ሁኔታዎች
የኢኮኖሚ እድገቱ ቢቀጥልም፣ ፖላንድ አሁንም እንደ ዝቅተኛ የልደት መጠን፣ የህዝብ ቁጥር እርጅና እና ከገጠርና ከተማ ያለውን የልማት ልዩነት የመሳሰሉ ፈተናዎች ከፊቷ አሉ። ሆኖም እንደ ካዚሚዬርዝ ፋላክ ያሉ ወጣቶች ሀገሪቱ ያላትን ተስፋ በማየት እዚያው ለመቆየት መርጠዋል። "ፖላንድ ተስፋ ያላት ሀገር ናት" ይላል።
ምንጭ፦AP / DH
በ1989 የኮሚኒዝም ውድቀትን ተከትሎ የፖላንድ ኢኮኖሚ አስገራሚ ለውጥ አሳይቷል። በአንድ ወቅት ደካማና ያልተረጋጋ የነበረው ኢኮኖሚዋ፣ ዛሬ በአውሮፓ ውስጥ ስኬታማ ከሚባሉት አንዱ ሆኗል።
ከአንድ ትውልድ በፊት በፖላንድ ስኳር እና ዱቄት የሚገዙት በኩፖን ነበር፤ ዜጎቿም ከምዕራብ ጀርመናውያን ጋር ሲነጻጸር የአስረኛ እጅ ያህል ብቻ ነበር የሚያገኙት። ዛሬ ግን የሀገሪቱ ኢኮኖሚ ስዊዘርላንድን በመቅደም፣ ከቢሊዮን ዶላር በላይ ዓመታዊ የሀገር ውስጥ ምርት (GDP) በማስመዝገብ በዓለም 20ኛው ግዙፍ ኢኮኖሚ ለመሆን በቅቷል።
ይህ ከ1989-90 የኮሚኒዝም ፍርስራሽ ተነስተው ወደ አውሮፓ የእድገት ሻምፒዮንነት የተደረገ ታሪካዊ ዝላይ ነው - ይህም ለተራው ህዝብ ብልጽግናን እንዴት ማምጣት እንደሚቻል ትምህርት የሚሰጥ መሆኑን ኢኮኖሚስቶች ይናገራሉ።
የዶናልድ ትራምፕ አስተዳደርም ይህ ዕውቅና ሊሰጠው ይገባል በሚል ፖላንድ በቀጣይ ዓመት በሚካሄደው የቡድን 20 ጉባኤ ላይ እንድትጋበዝ ፍላጎት አለው።
ይህ ለውጥ እንደ ጆአና ኮዋልስካ ባሉ ሰዎች ሕይወት ውስጥ ይንጸባረቃል። በበርሊን እና በዋርሶ መካከል በምትገኘው ፖዝናን ከተማ ውስጥ መሃንዲስ የሆነችው ጆአና፣ በአሜሪካ ለአምስት ዓመታት ከቆየች በኋላ ወደ ሀገሯ ተመልሳለች።
"ወደ ፖላንድ ከተመለስኩ በኋላ የሚናፍቀኝ ነገር እንዳለ ብዙ ጊዜ እጠየቃለሁ፣ እውነቱን ለመናገር ግን ተቃራኒው ነው የሚሰማኝ" ትላለች። "በብዙ ዘርፎች ከአሜሪካ ቀድመን እንገኛለን።"
ኮዋልስካ በፖዝናን የሱፐር ኮምፒውቲንግ እና ኔትወርክ ማእከል ውስጥ ትሰራለች። ማእከሉ በፖላንድ የመጀመሪያውን አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ (AI) ፋብሪካ እያለማ ሲሆን፣ በአውሮፓ ህብረት ከሚደገፉ አስር የኳንተም ኮምፒውተሮች አንዱ ጋርም እያገናኘው ይገኛል።
በፖዝናን ቴክኒካል ዩኒቨርሲቲ ከተመረቀች በኋላ በአሜሪካ ማይክሮሶፍት ውስጥ የሰራች ቢሆንም፣ "የተልዕኮ ስሜት" ይጎድላት እንደነበር ትናገራለች። "በተለይ በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ረገድ ቴክኖሎጂው በፖላንድ በሚገርም ፍጥነት እያደገ ነው፤ ለዚህም ነው መመለሱ በጣም የሳበኝ" ትላለች።
ከድህነት መውጣት
ለቡድን 20 ጉባኤ የቀረበው ግብዣ ትልቅ ትርጉም ያለው ቢሆንም፣ እስካሁን በንግድ ቡድኑ ውስጥ እንግዳ ሀገር ሙሉ አባል የሆነችበት አጋጣሚ የለም። ሆኖም ግን አሃዞቹ የራሳቸውን ታሪክ ይናገራሉ፦ በ35 ዓመታት ውስጥ የፖላንድ የነፍስ ወከፍ ገቢ በ2025 ወደ 55,340 ዶላር አድጓል፣ ይህም የአውሮፓ ህብረት አማካይ 85% ነው።
በ1990 ከነበረበት 6,730 ዶላር ሲነጻጸር ግዙፍ ዝላይ ሲሆን፣ አሁን በዓለም አቀፍ የገንዘብ ድርጅት (IMF) መረጃ መሠረት ከጃፓን (52,039 ዶላር) ጋር እኩል ደረጃ ላይ ትገኛለች።
ፖላንድ እ.ኤ.አ. በ2004 የአውሮፓ ህብረትን ከተቀላቀለች በኋላ፣ ኢኮኖሚዋ በአማካይ በዓመት 3.8% አድጓል፤ ይህም ከአውሮፓ አማካይ 1.8% በእጥፍ ይበልጣል።
እንደ ማርሲን ፒዮንትኮቭስኪ ገለጻ፣ ለዚህ ስኬት ቁልፉ አንድ ምክንያት ብቻ አይደለም። ዋነኞቹ ምክንያቶች የሚከተሉት ናቸው፦
ጠንካራ ተቋማት፦ ገለልተኛ የዳኝነት አካል፣ ፍትሃዊ ውድድርን የሚያረጋግጥ የፀረ-ሞኖፖሊ ተቋም እና የባንክ ቀውስን የሚከላከሉ ጠንካራ ደንቦች።
ሙስናን መከላከል፦ ለተቋማቱ ጥንካሬ ምስጋና ይግባውና እንደሌሎች የቀድሞ ኮሚኒስት ሀገራት ኢኮኖሚው በሙስና እና በባለሀብቶች አልተመዘበረም።
የአውሮፓ ህብረት ድጋፍ፦ ከህብረቱ የተገኘው በቢሊዮን የሚቆጠር ዩሮ እርዳታ እና የጋራ ገበያ ተጠቃሚነት።
ፖለቲካዊ ስምምነት፦ የርዕዮተ ዓለም ልዩነት ሳይገድባቸው፣ ሁሉም የፖለቲካ ኃይሎች ወደ አውሮፓ ህብረት የመግባት የረጅም ጊዜ ግብ ላይ ተስማምተው መቆየታቸው።
"ፖላንዳውያን ወዴት እንደሚሄዱ ያውቁ ነበር" ይላሉ ፒዮንትኮቭስኪ። ምዕራባውያን ለ500 ዓመታት ያዳበሩትን የተቋማት አሰራር እና ህጎችን ፖላንድ በአጭር ጊዜ ወስዳ ተግባራዊ አድርጋለች።
የሶላሪስ ኩባንያ ስኬት
በ1996 በፖዝናን የተመሰረተው የሶላሪስ ኩባንያ፣ ዛሬ 15% የገበያ ድርሻ በመያዝ በአውሮፓ ግንባር ቀደም የኤሌክትሪክ አውቶቡስ አምራች ነው።
ይህ ኩባንያ የፖላንድን የስራ ፈጣሪነት እና የፈጠራ ብቃት ማሳያ ነው። እ.ኤ.አ. በ2011 ገና በአውሮፓ የኤሌክትሪክ ቴክኖሎጂ ባልተለመደበት ወቅት ምርቱን በመጀመሩ የቴክኖሎጂ መሪ መሆን ችሏል።
ፈታኝ ሁኔታዎች
የኢኮኖሚ እድገቱ ቢቀጥልም፣ ፖላንድ አሁንም እንደ ዝቅተኛ የልደት መጠን፣ የህዝብ ቁጥር እርጅና እና ከገጠርና ከተማ ያለውን የልማት ልዩነት የመሳሰሉ ፈተናዎች ከፊቷ አሉ። ሆኖም እንደ ካዚሚዬርዝ ፋላክ ያሉ ወጣቶች ሀገሪቱ ያላትን ተስፋ በማየት እዚያው ለመቆየት መርጠዋል። "ፖላንድ ተስፋ ያላት ሀገር ናት" ይላል።
ምንጭ፦AP / DH
5 months ago
እራሱ ሰረቀ ። ለፖሊስም አመለከተ... የገዛ ራሱን ያስያዘው ዘራፊ
እ.ኤ.አ. በ1996 በካሊፎርኒያ የሚገኝ የሱቅ ስራ አስኪያጅ የነበረው ሼን ሚካኤል ላታ፣ የገዛ ራሱን ሱቅ በመዝረፍ ለፖሊስ "ተዘረፍኩ" በማለት ሀሰተኛ ሪፖርት አደረገ።
ለፖሊስ ይህ ሰው የሰጠውን መረጃ ተገን በማድረግ ስዕል ባለሙያ የሳለው ስዕል ተዘረፍኩ ካለው ሰው ጋር ፍጹም ተመሳሳይ ሆነ።
ፖሊሶች ስዕሉን አይተው "ይህ አንተኑ ነው ሚመስለው ሲሉት " ሲሉት ድርጊቱን አመነ።
ምንጭ፦ ሎስ አንጀለስ ታይምስ
እ.ኤ.አ. በ1996 በካሊፎርኒያ የሚገኝ የሱቅ ስራ አስኪያጅ የነበረው ሼን ሚካኤል ላታ፣ የገዛ ራሱን ሱቅ በመዝረፍ ለፖሊስ "ተዘረፍኩ" በማለት ሀሰተኛ ሪፖርት አደረገ።
ለፖሊስ ይህ ሰው የሰጠውን መረጃ ተገን በማድረግ ስዕል ባለሙያ የሳለው ስዕል ተዘረፍኩ ካለው ሰው ጋር ፍጹም ተመሳሳይ ሆነ።
ፖሊሶች ስዕሉን አይተው "ይህ አንተኑ ነው ሚመስለው ሲሉት " ሲሉት ድርጊቱን አመነ።
ምንጭ፦ ሎስ አንጀለስ ታይምስ
5 months ago
''የሰውየው ጥልማሞት''
🇷🇺 ሰላይነት እስከ ክሬምሊን ቤተ-መንግሥት፦ የቭላድሚር ፑቲን የሩብ ምዕተ-ዓመት ጉዞ!
#ethiopia | "ከታች ተነስቶ ለታላቅነት" ለሚለው አባባል የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ፍጹም ማሳያ ናቸው። ለሩብ ምዕተ-ዓመት የዓለምን ፖለቲካ ሲያናውጡ የቆዩት ፑቲን፣ ከሶቪየት ህብረት ውድቀት በኋላ ሩሲያን ዳግም ልዕለ-ኃያል ወደ መሆን የመለሱ መሪ ተደርገው ይወሰዳሉ።
🕵️♂️ ከስለላ ዓለም ወደ ፖለቲካ ማማ
ፑቲን የፖለቲካ ሕይወታቸውን የጀመሩት በታዋቂው የሶቪየት የስለላ ድርጅት ኬ.ጂ.ቢ (KGB) ውስጥ በሰላይነት ነበር። እ.ኤ.አ በ1991 ሶቪየት ህብረት ስትፈርስ፣ ወደ ትውልድ ከተማቸው ሴንት ፒተርስበርግ በመመለስ የከተማዋ ምክትል ከንቲባ በመሆን የሥልጣን እርካባቸውን መርገጥ ጀመሩ።
🚀 የሞስኮው ፈጣን ዕድገት
እ.ኤ.አ በ1996 ወደ ሞስኮ ያመሩት ፑቲን፣ በፕሬዝዳንት ቦሪስ የልሲን አስተዳደር ውስጥ በነበራቸው ታማኝነት በፍጥነት የደረጃ ዕድገት አገኙ። የሀገሪቱን የደህንነት መዋቅር (FSB) እንዲቆጣጠሩ ከተደረገ በኋላ፣ በ1999 የልሲን በድንገት ሥልጣን ሲለቁ ፑቲን ተተኪ መሆናቸው በይፋ ታወጀ። ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ለ26 ዓመታት ሩሲያን በፕሬዝዳንትነት እና በጠቅላይ ሚኒስትርነት እየመሩ ይገኛሉ።
🔄 የሥልጣን ማራዘሚያ ስልቶች (Zeroing Out)
ፑቲን የሥልጣን ገደብን ለማለፍ የተለያዩ "ብልህ" ስልቶችን ተጠቅመዋል
* የ2008 ስትራቴጂ፦ የሥልጣን ዘመናቸው ሲያበቃ የቅርብ ወዳጃቸውን ዲሚትሪ ሜድቬዴቭን ፕሬዝዳንት አድርገው በመሾም፣ እሳቸው ደግሞ ጠቅላይ ሚኒስትር በመሆን ሀገሪቱን ከጀርባ ሆነው መርተዋል።
* የ"ዜሮ" ማሻሻያ፦ በቅርቡ በተደረገ ሕገ-መንግሥታዊ ማሻሻያ፣ ቀደም ሲል ያገለገሉባቸው ዓመታት "እንደማይቆጠሩ" በማድረግ እስከ እ.ኤ.አ 2036 ድረስ በሥልጣን ላይ የመቆየት ሕጋዊ ዕድል ፈጥረዋል።
በወቅቱ የ83 ዓመት አዛውንት የሚሆኑት ፑቲን፣ አስፈላጊ ከሆነ ሕጉን ደግመው በማሻሻል ዕድሜ ልካቸውን መሪ የመሆን ዕድል እንዳላቸው የፖለቲካ ተንታኞች ይናገራሉ። የፑቲን ታሪክ የፖለቲካ ብልህነትን እና ሕገ-መንግሥታዊ ማዕቀፎችን ለሥልጣን ማቆያነት እንዴት መጠቀም እንደሚቻል ትልቅ ትምህርት የሚሰጥ ነው።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #መናኸሪያFM #vladimirputin #russia #kremlin #kgb #politics #worldnews #succession #constitutionalreform #globalpolitics #history
🇷🇺 ሰላይነት እስከ ክሬምሊን ቤተ-መንግሥት፦ የቭላድሚር ፑቲን የሩብ ምዕተ-ዓመት ጉዞ!
#ethiopia | "ከታች ተነስቶ ለታላቅነት" ለሚለው አባባል የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ፍጹም ማሳያ ናቸው። ለሩብ ምዕተ-ዓመት የዓለምን ፖለቲካ ሲያናውጡ የቆዩት ፑቲን፣ ከሶቪየት ህብረት ውድቀት በኋላ ሩሲያን ዳግም ልዕለ-ኃያል ወደ መሆን የመለሱ መሪ ተደርገው ይወሰዳሉ።
🕵️♂️ ከስለላ ዓለም ወደ ፖለቲካ ማማ
ፑቲን የፖለቲካ ሕይወታቸውን የጀመሩት በታዋቂው የሶቪየት የስለላ ድርጅት ኬ.ጂ.ቢ (KGB) ውስጥ በሰላይነት ነበር። እ.ኤ.አ በ1991 ሶቪየት ህብረት ስትፈርስ፣ ወደ ትውልድ ከተማቸው ሴንት ፒተርስበርግ በመመለስ የከተማዋ ምክትል ከንቲባ በመሆን የሥልጣን እርካባቸውን መርገጥ ጀመሩ።
🚀 የሞስኮው ፈጣን ዕድገት
እ.ኤ.አ በ1996 ወደ ሞስኮ ያመሩት ፑቲን፣ በፕሬዝዳንት ቦሪስ የልሲን አስተዳደር ውስጥ በነበራቸው ታማኝነት በፍጥነት የደረጃ ዕድገት አገኙ። የሀገሪቱን የደህንነት መዋቅር (FSB) እንዲቆጣጠሩ ከተደረገ በኋላ፣ በ1999 የልሲን በድንገት ሥልጣን ሲለቁ ፑቲን ተተኪ መሆናቸው በይፋ ታወጀ። ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ለ26 ዓመታት ሩሲያን በፕሬዝዳንትነት እና በጠቅላይ ሚኒስትርነት እየመሩ ይገኛሉ።
🔄 የሥልጣን ማራዘሚያ ስልቶች (Zeroing Out)
ፑቲን የሥልጣን ገደብን ለማለፍ የተለያዩ "ብልህ" ስልቶችን ተጠቅመዋል
* የ2008 ስትራቴጂ፦ የሥልጣን ዘመናቸው ሲያበቃ የቅርብ ወዳጃቸውን ዲሚትሪ ሜድቬዴቭን ፕሬዝዳንት አድርገው በመሾም፣ እሳቸው ደግሞ ጠቅላይ ሚኒስትር በመሆን ሀገሪቱን ከጀርባ ሆነው መርተዋል።
* የ"ዜሮ" ማሻሻያ፦ በቅርቡ በተደረገ ሕገ-መንግሥታዊ ማሻሻያ፣ ቀደም ሲል ያገለገሉባቸው ዓመታት "እንደማይቆጠሩ" በማድረግ እስከ እ.ኤ.አ 2036 ድረስ በሥልጣን ላይ የመቆየት ሕጋዊ ዕድል ፈጥረዋል።
በወቅቱ የ83 ዓመት አዛውንት የሚሆኑት ፑቲን፣ አስፈላጊ ከሆነ ሕጉን ደግመው በማሻሻል ዕድሜ ልካቸውን መሪ የመሆን ዕድል እንዳላቸው የፖለቲካ ተንታኞች ይናገራሉ። የፑቲን ታሪክ የፖለቲካ ብልህነትን እና ሕገ-መንግሥታዊ ማዕቀፎችን ለሥልጣን ማቆያነት እንዴት መጠቀም እንደሚቻል ትልቅ ትምህርት የሚሰጥ ነው።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #መናኸሪያFM #vladimirputin #russia #kremlin #kgb #politics #worldnews #succession #constitutionalreform #globalpolitics #history
Sponsored by
Surafel
6 months ago
ከእስረኝነት ወደ ጠበቃነት፡ በግፍ የታሰረውና ዳኛውን ለፍርድ ያቀረበው ግለሰብ አስገራሚ ታሪክ!
ታሪኩ የሳንቾዝ ቶማስ ነው። ይህ ሰው ያልሰራውን ወንጀል ሰርተሃል ተብሎ በቁም እስራት (Life sentence) ተፈርዶበት ለ10 ዓመታት በእስር ቤት አሳልፏል።
ነገር ግን ተስፋ ከመቁረጥ ይልቅ ፍትህን በገዛ እጁ ለማምጣት ወሰነ።
📌 ዋና ዋና ነጥቦች፦
እስራቱ፡ እ.ኤ.አ በ1991 አይዛክ ራይት ጁኒየር በኒው ጀርሲ ግዛት "የአደንዛዥ ዕፅ ንጉስ" ተብሎ በፈጠራ ክስ ተፈረደበት።
በትምህርት የታጠቀው ትግል፡ በእስር ቤት እያለ የህግ ትምህርትን በከፍተኛ ጥረት አጠና። የራሱን መዝገብ ብቻ ሳይሆን የሌሎች 20 የሚሆኑ አብረውት የታሰሩ ንጹሃንን መዝገብ በመመርመር ነፃ እንዲወጡ አድርጓል።
ድሉ፡ እ.ኤ.አ በ1996 አይዛክ ራይት ራሱን ወክሎ በመከራከር፣ ፖሊሶች እና አቃቤ ህግ የሀሰት ምስክር ማቅረባቸውን አረጋገጠ። በዚህም ከእስር ነፃ ወጣ።
የዳኛው እጣ ፈንታ፡ ክሱን የመራው ዳኛ ኒኮላስ ቢሲል ሙስና እና ሌሎች ወንጀሎች ላይ ተባባሪ መሆኑ ተረጋግጦ ሊታሰር ሲል ራሱን አጥፍቷል።
አይዛክ ግን ትግሉን ቀጥሎ በ2017 በይፋ የጠበቃነት ፍቃዱን አግኝቷል።
ታሪኩ የሳንቾዝ ቶማስ ነው። ይህ ሰው ያልሰራውን ወንጀል ሰርተሃል ተብሎ በቁም እስራት (Life sentence) ተፈርዶበት ለ10 ዓመታት በእስር ቤት አሳልፏል።
ነገር ግን ተስፋ ከመቁረጥ ይልቅ ፍትህን በገዛ እጁ ለማምጣት ወሰነ።
📌 ዋና ዋና ነጥቦች፦
እስራቱ፡ እ.ኤ.አ በ1991 አይዛክ ራይት ጁኒየር በኒው ጀርሲ ግዛት "የአደንዛዥ ዕፅ ንጉስ" ተብሎ በፈጠራ ክስ ተፈረደበት።
በትምህርት የታጠቀው ትግል፡ በእስር ቤት እያለ የህግ ትምህርትን በከፍተኛ ጥረት አጠና። የራሱን መዝገብ ብቻ ሳይሆን የሌሎች 20 የሚሆኑ አብረውት የታሰሩ ንጹሃንን መዝገብ በመመርመር ነፃ እንዲወጡ አድርጓል።
ድሉ፡ እ.ኤ.አ በ1996 አይዛክ ራይት ራሱን ወክሎ በመከራከር፣ ፖሊሶች እና አቃቤ ህግ የሀሰት ምስክር ማቅረባቸውን አረጋገጠ። በዚህም ከእስር ነፃ ወጣ።
የዳኛው እጣ ፈንታ፡ ክሱን የመራው ዳኛ ኒኮላስ ቢሲል ሙስና እና ሌሎች ወንጀሎች ላይ ተባባሪ መሆኑ ተረጋግጦ ሊታሰር ሲል ራሱን አጥፍቷል።
አይዛክ ግን ትግሉን ቀጥሎ በ2017 በይፋ የጠበቃነት ፍቃዱን አግኝቷል።
7 months ago
በፈረንሳይ የሚታወቁት ፖለቲከኛ እና የቀድሞ የእግር ኳስ ክለብ ፕሬዝዳንት በእናታቸው የቀብር ሥነ-ሥርዓት ላይ ተገደሉ
የኮርሲካ ተገንጣይ ቡድን መሪ እና የቀድሞው የኤሲ አጃክሲዮ (AC Ajaccio) እግር ኳስ ክለብ ፕሬዝዳንት የነበሩት አላይን ኦርሶኒ (Alain Orsoni)፤ ትናንት ሰኞ በእናታቸው የቀብር ሥነ-ሥርዓት ላይ እያሉ በታጣቂዎች ተገደሉ።
እንደ ፈረንሳዩ ሌ ሞንድ ጋዜጣ ዘገባ ከሆነ፣ ግድያው የተፈጸመው በደቡባዊ ኮርሲካ በሚገኘው "ቬሮ" በተሰኘው የትውልድ መንደራቸው ውስጥ ነው። ኦርሶኒ ለእናታቸው የመጨረሻ ሽኝት እያደረጉ ባለበት ወቅት በደረሰባቸው ጥቃት ህይወታቸው አልፏል።
የአከባቢው አቃቤ ህግ ኒኮላስ ሴፕት እንደገለጹት፣ ስለ ግድያው ሰፊ ምርመራ በፖሊስ ተጀምሯል። ጉዳዩም በማርሴይ ለሚገኘው ክልላዊ ፍርድ ቤት በይፋ ተመርቷል።
አላይን ኦርሶኒ በኮርሲካ ፖለቲካ ውስጥ ረጅም እና አወዛጋቢ ታሪክ ያላቸው ሰው ናቸው።
በ1980ዎቹ የኮርሲካ ብሔራዊ ነፃነት ግንባር (FLNC) መሪዎች አንዱ ነበሩ ። በኋላም የራስን ዕድል በራስ የመወሰን ንቅናቄን (MPA) መርተዋል።
በፈረንጆቹ ከ2008 እስከ 2015 ድረስ የኤሲ አጃክሲዮ እግር ኳስ ክለብ ፕሬዝዳንት በመሆን አገልግለዋል።
በአማጺያን ንቅናቄው ውስጥ በነበረው ከፍተኛ ውጥረት ምክንያት ኦርሶኒ በ1996 ኮርሲካን ለቀው ለመውጣት ተገድደው ነበር። ለ13 ዓመታት በፍሎሪዳ፣ በኒካራጓ እና በስፔን በስደት ከቆዩ በኋላ ነበር ወደ ደሴቷ የተመለሱት።
ኦርሶኒ ከዚህ ቀደምም በ2008 ዓ.ም የግድያ ሙከራ ተደርጎባቸው የነበረ ሲሆን፣ ወንድማቸው ጊጅ ኦርሶኒ በ1983 መገደሉ ይታወሳል። ኦርሶኒም ልጃቸውን በሟች ወንድማቸው ስም ሰይመውት ነበር።
የኮርሲካ ተገንጣይ ቡድን መሪ እና የቀድሞው የኤሲ አጃክሲዮ (AC Ajaccio) እግር ኳስ ክለብ ፕሬዝዳንት የነበሩት አላይን ኦርሶኒ (Alain Orsoni)፤ ትናንት ሰኞ በእናታቸው የቀብር ሥነ-ሥርዓት ላይ እያሉ በታጣቂዎች ተገደሉ።
እንደ ፈረንሳዩ ሌ ሞንድ ጋዜጣ ዘገባ ከሆነ፣ ግድያው የተፈጸመው በደቡባዊ ኮርሲካ በሚገኘው "ቬሮ" በተሰኘው የትውልድ መንደራቸው ውስጥ ነው። ኦርሶኒ ለእናታቸው የመጨረሻ ሽኝት እያደረጉ ባለበት ወቅት በደረሰባቸው ጥቃት ህይወታቸው አልፏል።
የአከባቢው አቃቤ ህግ ኒኮላስ ሴፕት እንደገለጹት፣ ስለ ግድያው ሰፊ ምርመራ በፖሊስ ተጀምሯል። ጉዳዩም በማርሴይ ለሚገኘው ክልላዊ ፍርድ ቤት በይፋ ተመርቷል።
አላይን ኦርሶኒ በኮርሲካ ፖለቲካ ውስጥ ረጅም እና አወዛጋቢ ታሪክ ያላቸው ሰው ናቸው።
በ1980ዎቹ የኮርሲካ ብሔራዊ ነፃነት ግንባር (FLNC) መሪዎች አንዱ ነበሩ ። በኋላም የራስን ዕድል በራስ የመወሰን ንቅናቄን (MPA) መርተዋል።
በፈረንጆቹ ከ2008 እስከ 2015 ድረስ የኤሲ አጃክሲዮ እግር ኳስ ክለብ ፕሬዝዳንት በመሆን አገልግለዋል።
በአማጺያን ንቅናቄው ውስጥ በነበረው ከፍተኛ ውጥረት ምክንያት ኦርሶኒ በ1996 ኮርሲካን ለቀው ለመውጣት ተገድደው ነበር። ለ13 ዓመታት በፍሎሪዳ፣ በኒካራጓ እና በስፔን በስደት ከቆዩ በኋላ ነበር ወደ ደሴቷ የተመለሱት።
ኦርሶኒ ከዚህ ቀደምም በ2008 ዓ.ም የግድያ ሙከራ ተደርጎባቸው የነበረ ሲሆን፣ ወንድማቸው ጊጅ ኦርሶኒ በ1983 መገደሉ ይታወሳል። ኦርሶኒም ልጃቸውን በሟች ወንድማቸው ስም ሰይመውት ነበር።
7 months ago
እግረኞች ተገቢ ባልሆነ የመንገድ አጠቃቀም የሕግ ተጠያቂነት እንደሚደርስባቸው ያውቃሉ?
#ethiopia | የትራፊክ አደጋ በአሁኑ ወቅት አሳሳቢ ደረጃ ላይ ይገኛል። ይህ አደጋ ለአካል ጉዳተኝነትና ሕይወትን እስከማጣት የሚያደርስ ከባድ ዋጋ ያስከፍላል።
ለትራፊክ አደጋ ዋነኛው ምክንያት የአሽከርካሪዎች ስህተት እንደሆነ ቢነገርም፣ በእግረኞች በኩል የሚታዩ ክፍተቶችም ሚናቸው ላቅ ያለ ነው።
የኮሪደር ልማት ሥራዎች መንገዶችን ለእግረኞች ምቹ እንዲሆኑ አስችለዋል፤ ሆኖም ግን አሁንም እግረኞች የተፈቀደላቸውን መሻገሪያዎች ባለመጠቀም ለከፋ ጉዳት ሲዳረጉ ይታያል።
በአስፓልት መሃል መጓዝ፣ በተዘጋጀ የእግረኛ ድልድይ አለመሻገርና የመሳሰሉ ሕገ-ወጥ ተግባራትም ይስተዋላሉ።
የሕግ ባለሙያና ተመራማሪ የሆኑት አቶ አብዱራዛቅ ነስሩ ከኢቲቪ ጋር በነበራቸው ቆይታ፤ የመንገድ ዳር ብረት መዝለልና በተፈቀደው አግባብ አለመጓዝ የሕግ ተጠያቂነት እንደሚያስከትል ገልጸዋል።
አብዛኛውን ጊዜ በመኪና አደጋ ጉዳይ አሽከርካሪዎች ብቻ ሲጠየቁ መስማት የተለመደ ቢሆንም፣ የእግረኞች ኃላፊነትም ምን መሆን አለበት የሚለው አብሮ መነሳት እንዳለበት ባለሙያው ጠቁመዋል። ለእግረኛ ቅድሚያ መስጠት ተገቢ መሆኑ ቢታመንም፣ እግረኞችም መብታቸውን ሲጠቀሙ ግዴታቸውን ማክበር እንዳለባቸውም አንስተዋል።
ተሻሽሎ የጸደቀው የመንገድ ትራንስፖርት ትራፊክ መቆጣጠሪያ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ ቁጥር 557/2016 በእግረኞች ስለሚፈጸሙ የትራፊክ ጥሰቶች እንደሚደነግግ ጠቁመዋል።
ከዚህ በፊት የነበረው ሕግ አሽከርካሪዎች ላይ ብቻ ግዴታ የጣለ እንጂ እግረኞችን የማይከለክል እንደነበርም አያይዘው ገልጸዋል።
በአዲሱ ደንብ መሠረት ጥንቃቄ ሳያደርጉ መሻገር፣ ለተሽከርካሪ በተፈቀደ ቦታ ላይ መገኘት፣ ለእግረኛ ከተፈቀደው ቦታ ውጭ መንቀሳቀስ፣ በብረት ወይም በግንብ ከታጠሩ ቦታዎች መሻገር እንደሚያስቀጣም አስረድተዋል።
የገንዘብ ቅጣቱ አነስተኛ ቢሆንም፣ አሽከርካሪዎችም የራሳቸው ኃላፊነት እንዳለባቸው ባለሙያው ገልጸዋል።
በ1996 ዓ.ም የወጣውን የወንጀል ሕግ ዋቢ በማድረግ አሽከርካሪዎች አደጋ አድርሰው የእግረኛው ጥፋት ካለበትና በዚህም ምክንያት ሕይወት ቢያልፍ፣ ለአሽከርካሪው የሚወሰነው ቅጣት እንደሚቀንስለትም ባለሙያው አብራርተዋል።
በመሆኑም ከአደጋ ለመጠበቅ እና ከቅጣት ለመዳን እግረኞች ሕግን አክብረው በተፈቀደላቸው መንገድ ብቻ መጓዝ እንዳለባቸው የሕግ ባለሙያው ገልጸዋል።
#ebcdotstream
#ethiopia | የትራፊክ አደጋ በአሁኑ ወቅት አሳሳቢ ደረጃ ላይ ይገኛል። ይህ አደጋ ለአካል ጉዳተኝነትና ሕይወትን እስከማጣት የሚያደርስ ከባድ ዋጋ ያስከፍላል።
ለትራፊክ አደጋ ዋነኛው ምክንያት የአሽከርካሪዎች ስህተት እንደሆነ ቢነገርም፣ በእግረኞች በኩል የሚታዩ ክፍተቶችም ሚናቸው ላቅ ያለ ነው።
የኮሪደር ልማት ሥራዎች መንገዶችን ለእግረኞች ምቹ እንዲሆኑ አስችለዋል፤ ሆኖም ግን አሁንም እግረኞች የተፈቀደላቸውን መሻገሪያዎች ባለመጠቀም ለከፋ ጉዳት ሲዳረጉ ይታያል።
በአስፓልት መሃል መጓዝ፣ በተዘጋጀ የእግረኛ ድልድይ አለመሻገርና የመሳሰሉ ሕገ-ወጥ ተግባራትም ይስተዋላሉ።
የሕግ ባለሙያና ተመራማሪ የሆኑት አቶ አብዱራዛቅ ነስሩ ከኢቲቪ ጋር በነበራቸው ቆይታ፤ የመንገድ ዳር ብረት መዝለልና በተፈቀደው አግባብ አለመጓዝ የሕግ ተጠያቂነት እንደሚያስከትል ገልጸዋል።
አብዛኛውን ጊዜ በመኪና አደጋ ጉዳይ አሽከርካሪዎች ብቻ ሲጠየቁ መስማት የተለመደ ቢሆንም፣ የእግረኞች ኃላፊነትም ምን መሆን አለበት የሚለው አብሮ መነሳት እንዳለበት ባለሙያው ጠቁመዋል። ለእግረኛ ቅድሚያ መስጠት ተገቢ መሆኑ ቢታመንም፣ እግረኞችም መብታቸውን ሲጠቀሙ ግዴታቸውን ማክበር እንዳለባቸውም አንስተዋል።
ተሻሽሎ የጸደቀው የመንገድ ትራንስፖርት ትራፊክ መቆጣጠሪያ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ ቁጥር 557/2016 በእግረኞች ስለሚፈጸሙ የትራፊክ ጥሰቶች እንደሚደነግግ ጠቁመዋል።
ከዚህ በፊት የነበረው ሕግ አሽከርካሪዎች ላይ ብቻ ግዴታ የጣለ እንጂ እግረኞችን የማይከለክል እንደነበርም አያይዘው ገልጸዋል።
በአዲሱ ደንብ መሠረት ጥንቃቄ ሳያደርጉ መሻገር፣ ለተሽከርካሪ በተፈቀደ ቦታ ላይ መገኘት፣ ለእግረኛ ከተፈቀደው ቦታ ውጭ መንቀሳቀስ፣ በብረት ወይም በግንብ ከታጠሩ ቦታዎች መሻገር እንደሚያስቀጣም አስረድተዋል።
የገንዘብ ቅጣቱ አነስተኛ ቢሆንም፣ አሽከርካሪዎችም የራሳቸው ኃላፊነት እንዳለባቸው ባለሙያው ገልጸዋል።
በ1996 ዓ.ም የወጣውን የወንጀል ሕግ ዋቢ በማድረግ አሽከርካሪዎች አደጋ አድርሰው የእግረኛው ጥፋት ካለበትና በዚህም ምክንያት ሕይወት ቢያልፍ፣ ለአሽከርካሪው የሚወሰነው ቅጣት እንደሚቀንስለትም ባለሙያው አብራርተዋል።
በመሆኑም ከአደጋ ለመጠበቅ እና ከቅጣት ለመዳን እግረኞች ሕግን አክብረው በተፈቀደላቸው መንገድ ብቻ መጓዝ እንዳለባቸው የሕግ ባለሙያው ገልጸዋል።
#ebcdotstream
7 months ago
እድሜያቸው 18 ዓመት ያልሞላ 5 ልጆችን ለስራ ስምሪት ወደ አውሮፓ ሀገራት እልካችኋለሁ በማለት ገንዘብ ሲቀበል የነበረ ግለሰብ በ12 ዓመት ፅኑ እስራት እና በገንዘብ ተቀጣ።
የቅጣት ውሳኔውን ያሳለፈው በፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት የልደታ ምድብ 20ኛ ወንጀል ችሎት ነው።
ግለሰቡ ንጋት አጠኔ በ1996 ዓ.ም የወጣውን የወንጀል ሕግ አንቀጽ 32 (1) ሀ እና በሰዉ የመነገድ እና ሰውን በህገወጥ መንገድ ድንበር የማሻገር ወንጀል ለመከላከል እና ለመቆጣጠር የወጣውን አዋጅ ቁጥር 1178/2012 አንቀጽ 8 (3) ስር የተመላከተዉን በመተላለፍ ክስ ቀርቦበታል።
በዚህም ተከሳሽ ካልተያዙ ግብረአበሮቹ ጋር በመሆን በቀጥታ ወይም በተዘዋዋሪ ገንዘብ ወይም ቁሳዊ ጥቅም ለማግኘት በማሰብ የግል ተበዳይ የሆነዉን ሕጻን አብዱልሳላም ሸሊላ ከኢትዮጵያ ወደ ሊቢያ ከዛም ወደ አውሮፓ እንደሚልከዉ ከማህበራዊ ሚዲያ መካከል አንዱ በሆነው በኢሞ በማውራት የማሳመን ስራ ሰርቷል፡፡
ከምራብ አርሲ ዞን ዶዶላ ወረዳ ኤዶ ከተማ ሰኔ 28 ቀን 2016 ዓ.ም ከግል ተበዳይ አብዱልሰላም ሙሃባ እና ፈልማታ መሃመድ ከተባለዉ ጋር ወደ አዲስ አበባ እንዲመጡ በማድረግ አዲስ አበባ ደርሰዉ ከኢሞ ባገኙት ስልክ ለተከሳሽ ደውለው በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ አዉቶቡስ ተራ ተገናኝተዉ ለመታወቂያ የሚሆን ፎቶ ግራፍ በስልክ አንስቶ ይዞ በመሄድ የአዲስ አበባ ነዋሪነት መታወቂያ ማዘጋጃ የሚሆን ከእያንዳንዳቸዉ 500 ብር ተቀብሏል፡፡
በሰኔ 29 ቀን 2016 ዓ.ም የአዲስ አበባ የነዋሪነት መታወቂያ ከአዲስ አበባ ወደ ጎንደር የሚሄዱበትን የአውሮፕላን ጉዞ ቲኬት እና ጎንደር ሲደርሱ የሚቀበላቸው ዳንኤል የሚባል የአባቱ ስም በትክክል የማይታወቅን ግለሰብ ስልክ ቁጥር በመስጠት እንዲሄዱ አድርጎ በተሰጠጣቸው ስልክ ቁጥር ደውለው ዳንኤል የተባለዉን ካገኙ በኋላ ከሌሎች ግብረ አበሮች ጋር በመሆን የግል ተበዳዮች የያዟቸውን የስልክ ቀፎዎች እና አዲስ አበባ የተሰጣቸዉን የነዋሪነት መታወቂያ በመቀበል እያንዳንዳቸው ብር 1 ሚሊየን 600 ሺህ ብር እንዲከፍሉ በመንገር ንጉስ ወደተባለ ሆቴል ወስደው አንድ ክፍል ውስጥ 6 ሆነዉ ለሶስት ቀናት እንዲኖሩ አድርገዋል።
አብዱልሰላም ሸሊላ የተባለውን የግል ተበዳይ ስም አለሙ አየለ ሃይማኖት ኦርቶዶክስ በሚል በመቀየር የጎንደር ከተማን የነዋሪነት መታወቂያ በመስጠት በሐምሌ 2 ቀን 2016 ዓ.ም ወደ መተማ ከተማ ከዚያም ወደ ሱዳን ሊቢያ እንዲሁም ወደ አውሮፓ ለማጓጓዝ ጎንደር አውሮፕላን ማረፊያ እንዳሉ በቤተሰቦቻቸው ክትትል አማካኝነት ተደርሶባቸው ሳይሄዱ የቀሩ በመሆኑ ተከሳሽ በፈጸመዉ ሰውን ድንበር ማሻገር ወንጀል ተከሷል፡፡
ተከሳሹ ህጻን አብዱልሰላም ሙሀባ፣ ህጻን አብዱልናስር ቃሲም፣ ህጻን ዩኔ ቃሲም እና ህጻን አብዱርሃማን ሁሴን በተባሉ ልጆች ላይ ተመሳሳይ የሆነ ድርጊት በመፈጸም በቀረበበት 5 ክስ በሶስቱ ጥፋተኛ ተብሏል።
በዚህም በ12 ዓመት እስራት እና በ8 ሺህ ብር ገንንዘብ መቀጮ እንዲቀጣ ተወስኗል።
FMC
የቅጣት ውሳኔውን ያሳለፈው በፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት የልደታ ምድብ 20ኛ ወንጀል ችሎት ነው።
ግለሰቡ ንጋት አጠኔ በ1996 ዓ.ም የወጣውን የወንጀል ሕግ አንቀጽ 32 (1) ሀ እና በሰዉ የመነገድ እና ሰውን በህገወጥ መንገድ ድንበር የማሻገር ወንጀል ለመከላከል እና ለመቆጣጠር የወጣውን አዋጅ ቁጥር 1178/2012 አንቀጽ 8 (3) ስር የተመላከተዉን በመተላለፍ ክስ ቀርቦበታል።
በዚህም ተከሳሽ ካልተያዙ ግብረአበሮቹ ጋር በመሆን በቀጥታ ወይም በተዘዋዋሪ ገንዘብ ወይም ቁሳዊ ጥቅም ለማግኘት በማሰብ የግል ተበዳይ የሆነዉን ሕጻን አብዱልሳላም ሸሊላ ከኢትዮጵያ ወደ ሊቢያ ከዛም ወደ አውሮፓ እንደሚልከዉ ከማህበራዊ ሚዲያ መካከል አንዱ በሆነው በኢሞ በማውራት የማሳመን ስራ ሰርቷል፡፡
ከምራብ አርሲ ዞን ዶዶላ ወረዳ ኤዶ ከተማ ሰኔ 28 ቀን 2016 ዓ.ም ከግል ተበዳይ አብዱልሰላም ሙሃባ እና ፈልማታ መሃመድ ከተባለዉ ጋር ወደ አዲስ አበባ እንዲመጡ በማድረግ አዲስ አበባ ደርሰዉ ከኢሞ ባገኙት ስልክ ለተከሳሽ ደውለው በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ አዉቶቡስ ተራ ተገናኝተዉ ለመታወቂያ የሚሆን ፎቶ ግራፍ በስልክ አንስቶ ይዞ በመሄድ የአዲስ አበባ ነዋሪነት መታወቂያ ማዘጋጃ የሚሆን ከእያንዳንዳቸዉ 500 ብር ተቀብሏል፡፡
በሰኔ 29 ቀን 2016 ዓ.ም የአዲስ አበባ የነዋሪነት መታወቂያ ከአዲስ አበባ ወደ ጎንደር የሚሄዱበትን የአውሮፕላን ጉዞ ቲኬት እና ጎንደር ሲደርሱ የሚቀበላቸው ዳንኤል የሚባል የአባቱ ስም በትክክል የማይታወቅን ግለሰብ ስልክ ቁጥር በመስጠት እንዲሄዱ አድርጎ በተሰጠጣቸው ስልክ ቁጥር ደውለው ዳንኤል የተባለዉን ካገኙ በኋላ ከሌሎች ግብረ አበሮች ጋር በመሆን የግል ተበዳዮች የያዟቸውን የስልክ ቀፎዎች እና አዲስ አበባ የተሰጣቸዉን የነዋሪነት መታወቂያ በመቀበል እያንዳንዳቸው ብር 1 ሚሊየን 600 ሺህ ብር እንዲከፍሉ በመንገር ንጉስ ወደተባለ ሆቴል ወስደው አንድ ክፍል ውስጥ 6 ሆነዉ ለሶስት ቀናት እንዲኖሩ አድርገዋል።
አብዱልሰላም ሸሊላ የተባለውን የግል ተበዳይ ስም አለሙ አየለ ሃይማኖት ኦርቶዶክስ በሚል በመቀየር የጎንደር ከተማን የነዋሪነት መታወቂያ በመስጠት በሐምሌ 2 ቀን 2016 ዓ.ም ወደ መተማ ከተማ ከዚያም ወደ ሱዳን ሊቢያ እንዲሁም ወደ አውሮፓ ለማጓጓዝ ጎንደር አውሮፕላን ማረፊያ እንዳሉ በቤተሰቦቻቸው ክትትል አማካኝነት ተደርሶባቸው ሳይሄዱ የቀሩ በመሆኑ ተከሳሽ በፈጸመዉ ሰውን ድንበር ማሻገር ወንጀል ተከሷል፡፡
ተከሳሹ ህጻን አብዱልሰላም ሙሀባ፣ ህጻን አብዱልናስር ቃሲም፣ ህጻን ዩኔ ቃሲም እና ህጻን አብዱርሃማን ሁሴን በተባሉ ልጆች ላይ ተመሳሳይ የሆነ ድርጊት በመፈጸም በቀረበበት 5 ክስ በሶስቱ ጥፋተኛ ተብሏል።
በዚህም በ12 ዓመት እስራት እና በ8 ሺህ ብር ገንንዘብ መቀጮ እንዲቀጣ ተወስኗል።
FMC
8 months ago
የአዉስትራሊያ ባለስልጣናት የሀገሪቱን የጦር መሳሪያ ህጎችን ማጠናከር እንደሚያስፈልግ ገለፁ።
በሲድኒ ከተማ በአይሁዳውያን ሃኑካህ ክብረ በአል ላይ በተፈፀመ ጥቃት የ15 ያህል ሰዎች ህይወት ሲያልፍ፤ሌሎችም ለህይወታቸው አስጊ ሁኔታ ዉስጥ እንደሚገኙ እየተገለፀ ነዉ ።
የአዉስትራሊያ ባለስልጣናት ከዚህ ጥቃት በኋላ የሀገሪቱን የጦር መሣሪያ ህጎች ለማጠናከር ቃል መግባታቸዉን አሶሼትድ ኘሬስ ዘግቧል።
ቀድሞም ጥብቅ ነበር የተባለዉን የሀገሪቱ የጦር መሳሪያ ህግ ማሻሻል እንደሚያስፈልግ ባለስልጣናቱ ተናግረዋል ነዉ የተባለዉ።
ከሚወሰዱ አዳዲስ እርምጃዎች ዉስጥም የጦር መሳሪያ ብዛትን መገደብ እንዲሁም የተሰጡ ፍቃዶችን መገምገም እንደሆነ የዜና ወኪሉ አስነብቧል።
የሀገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትር አንቶኒ አልባኔስ፤ መንግስት አስፈላጊውን እርምጃ ለመዉሰድ ተዘጋጅቷል ብለዋል።
ለዚህም ጠንካራ የጦር መሳሪያ ህግ አስፈላጊ መሆኑን ተናግረዋል።
እ.ኤ.አ. በ1996 በታስማንያ አንድ ታጣቂ 35 ሰዎችን ከገደለ በኋላ በፍጥነት ተተኳሽ የሆኑ ጠመንጃዎችን ሀገሪቷ ማገዷን ዘገባዉ አስታዉሷል።
ከሰሞኑ በቦንዲ ባህር ዳርቻ የደረሰዉ ጥቃት በአውስትራሊያ ውስጥ በሦስት አስርት ዓመታት ውስጥ ከተከሰቱት እጅግ አስከፊው ጥቃት ነው ተብሏል።
ጥቃቱን የፈፀሙት አባት እና ልጅ በአውስትራሊያ አስደንጋጭ ማዕበልን የፈጠረ ጥቃትን እንዴት ሊፈጽሙ ቻሉ የሚለዉ እያነጋገረ ነዉ።
Ethio Fm
በሲድኒ ከተማ በአይሁዳውያን ሃኑካህ ክብረ በአል ላይ በተፈፀመ ጥቃት የ15 ያህል ሰዎች ህይወት ሲያልፍ፤ሌሎችም ለህይወታቸው አስጊ ሁኔታ ዉስጥ እንደሚገኙ እየተገለፀ ነዉ ።
የአዉስትራሊያ ባለስልጣናት ከዚህ ጥቃት በኋላ የሀገሪቱን የጦር መሣሪያ ህጎች ለማጠናከር ቃል መግባታቸዉን አሶሼትድ ኘሬስ ዘግቧል።
ቀድሞም ጥብቅ ነበር የተባለዉን የሀገሪቱ የጦር መሳሪያ ህግ ማሻሻል እንደሚያስፈልግ ባለስልጣናቱ ተናግረዋል ነዉ የተባለዉ።
ከሚወሰዱ አዳዲስ እርምጃዎች ዉስጥም የጦር መሳሪያ ብዛትን መገደብ እንዲሁም የተሰጡ ፍቃዶችን መገምገም እንደሆነ የዜና ወኪሉ አስነብቧል።
የሀገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትር አንቶኒ አልባኔስ፤ መንግስት አስፈላጊውን እርምጃ ለመዉሰድ ተዘጋጅቷል ብለዋል።
ለዚህም ጠንካራ የጦር መሳሪያ ህግ አስፈላጊ መሆኑን ተናግረዋል።
እ.ኤ.አ. በ1996 በታስማንያ አንድ ታጣቂ 35 ሰዎችን ከገደለ በኋላ በፍጥነት ተተኳሽ የሆኑ ጠመንጃዎችን ሀገሪቷ ማገዷን ዘገባዉ አስታዉሷል።
ከሰሞኑ በቦንዲ ባህር ዳርቻ የደረሰዉ ጥቃት በአውስትራሊያ ውስጥ በሦስት አስርት ዓመታት ውስጥ ከተከሰቱት እጅግ አስከፊው ጥቃት ነው ተብሏል።
ጥቃቱን የፈፀሙት አባት እና ልጅ በአውስትራሊያ አስደንጋጭ ማዕበልን የፈጠረ ጥቃትን እንዴት ሊፈጽሙ ቻሉ የሚለዉ እያነጋገረ ነዉ።
Ethio Fm
Sponsored by
Surafel
8 months ago
ሊከተሉት የሚገባ ሰው!
ሠዓሊና ቀራፂ ፕሮፌሰር በቀለ መኮንን
(ሂላሪያ ተስፋዬ እና ዕዝራ እጅጉ ተወዳጅ ሚድያ)
#ፕሮፌሰር በቀለመኮንን ለተወዳጅ ሚድያ የቅርብ ወዳጅና ቤተሰብ ነው። የምንሠራውን የስነዳ ፕሮጀክት በሙሉ ልብና መንፈስ የሚደግፍ ቀና ምሁር ነው። ታናሾቹን ለማገዝ በቀዳሚነት የሚሰለፍ ኩራት ያልፈጠረበት ታላቅ ወንድም እንደማለት ነው። ከ4 ዓመት አስቀድም "መዝገበ አእምሮ" ቅጽ አንድ ሲዘጋጅ ከጀርባ እና ከጎን ሆኖ ሲረዳን ነበር። የኃይሉ ልመንህን ታሪክ ፕሮፌሰር በቀለ አስታውሶ ታሪኩን ባይነግረን ኖሮ ኃይሉ ልመንህን አናገኘውም። ፕሮፌሰር በቀለ ሌሎችም ስሙን ከአክብሮት ጋር የሚያነሱት የሥነጥበብ ሰው ነው።
#ተወዳጅ ሚድያ እስከዛሬ የ432 ባለሙያዎችን ታሪክ በመፅሐፍ፣ በዲጂታል ሚድያ እና በድምፅ ሲሰንድ ፕሮፌሰር በቀለ መኮንንም እንዲካተት አድርጓል። እስከዛሬ በሚዲያ እና ኪነ-ጥበብ ዘርፍ የሠሩትን በምንችለው አቅም ታሪካቸው ዘመን እንዲሻገር ያደረግን ሲሆን የስነዳ ተግባሩም ተጠናክሮ ቀጥሏል። በቀጣይ እያዘጋጀነው ባለነው ዕትም ከ20 ዘርፎች የተውጣጡ ታላላቆችን በማሰባሰብ ላይ እንገኛለን ። ከእነዚህ ታላላቆች ውስጥ ፕሮፌሰር በቀለ መኮንን አንዱ ነው። የሕይወት ታሪኩንም ብዙ ካልታዩ የልጅነት ምስሎቹ ጋር አንድ ላይ በማድረግ ታሪኩን አጋርቶናል። ዕዝራ እጅጉ እና ሂላሪያ ተስፋዬም ታሪኩን እንደሚከተለው ሰንደውታል።በነገራችን ላይ በዚህ የሕይወት ታሪክ መጣጥፍ ውስጥ ተባባሪ ፕሮፌሰር ቴዎድርስ ገብሬ "በቀለን በብሔራዊ ትእምርት ፍለጋ ውስጥ" ብሎ የጻፈው ረዘም ያለ ምሁራዊ ትንተና አቅርበናል። የፕሮፌሰር በቀለ መምህር ወርቁ ጎሹ የሰጡትንም ምስክርነት አካተናል። መልካም ንባብ።
#የሰባተኛ ክፍል ተማሪ እያለ የስዕል ዝንባሌውን እንዲከተል እንዲሁም የስዕል ትምህርትን እንዲማር ያመለከቱትን መምህሩን በአንደበቱ ቃላት ይስላቸዋል። እኚህ መምህሩን፥ “ሊከተሉት የሚገባ ሰው” ሲል ይገልጻቸዋል። ምንአልባት ከበርካታ ዓመታት በኋላ እርሱ ራሱም እንዲያ ያለ ‘ሊከተሉት የሚገባ’ የጥበብ ሰው ሊሆን እንደሚችል አልገመተ ይሆናል።
#ፍላጎቱ ከእኩዮቹ የተለየ፣ ‘ተርታ’ ለሆነ ነገር መሻት የሌለው፣ በለጋ እድሜው ሳይቀር ነገሮችን እንደሆኑ ማየትና መሥራትን የማይመርጥ፣ አዲስ ነገር መፍጠርን አልያም የነበረውን በአዲስ መልክ መቃኘት ይቀናው የነበረ ተማሪ ነው። ስሙን ሳይቀር በስዕል ይጽፍ እንደነበር ይናገራል። በስጋው ላይ ያሠለጠናት ነፍሱ፥ ሰዓሊ የመሆን ግቡን ለማሳካት ይችል ዘንድ ‘የሰው ልጅ መሠረታዊ ነገሮችን’ አሻግሮ እንዲያይ ጉልበት ሰጥታዋለች። ይህ ጉልበትና ጽናት ነው፣ አሁን በሥነ ጥበብ ዘርፍ በኢትዮጵያ የመጀመሪያውን ሙሉ ፕሮፌሰር የወለደው፥ ሠዓሊና ቀራፂ ፕሮፌሰር በቀለ መኮንን።
#ትውልድና እድገቱ ደብረዘይት (ቢሾፍቱ) ከተማ ነው። ጥር 6 1956 ዓ.ም። ትምህርትን አሃዱ ያለው በቆሎ ትምህርት አቡጊዳ ብሎ ፊደል ቆጥሮ፣ ዳዊት ደግሞ ነው። የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርቱን አፄ ልብነ-ድንግል ወናግሰገድ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት፣ እንዲሁም ኹለተኛ ደረጃ ትምህርቱን በዚያው ደብረዘይት ልዕልት ተናኘወርቅ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተከታትሏል። የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ ፈተናውን የወሰደው ደግሞ በአዲስ አበባ ምኒልክ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ነው።
ከልጅነት እድሜው ጀምሮ የተገዛው ለስዕል ጥበብ ብቻ ሳይሆን በጠቅላላ ለጥበብ ነበር። አዲስ ነገርን አልያም የነበረው በተሻለ መንገድ ሆኖ ማየትን ይመርጣል። በጥበብ ለሚሠራ ነገር ሁሉ ልዩ ፍቅር አለው። አሁን በአዋቂነትና በርቱዕ አንደበቱ ውበት እንደሚገዛው፥ ሰው የማይሠራውን መሥራት አልያም የተሠራውን ነገር ባልተሠራበት መንገድ መሥራት እንደሚወድድ ይናገራል። ይህን ቃሉን በልጅነት እድሜው ሲገልጥ ደግሞ፣ ስሙን ሳይቀር በስዕል ይጽፍ ነበር።
#የተካነበት፣ የሠለጠነበትና የታወቀበት የስዕል እና የቅርጻ ቅርጽ ጥበብ ይሁን እንጂ፥ ለጽሑፍ ጥበብ እና ውበትም ስሱ ነው። በልጅነትና ወጣትነት እድሜው በደብረዘይት ኪነት ውስጥ ቴአትር፣ ግጥም እንዲሁም መፈክር ጭምር በመጻፍ ይታወቃል። እንደውም ለተማሪዎች፣ ለሰፈሩ ወጣቶች የጻፋቸው የፍቅር ብሎም ልዩ ልዩ ደብዳቤዎችና ግጥሞች ጋር በተያያዘ በተለያየ አጋጣሚ የሚያነሳቸው ገጠመኞቹ ጥቂት አይደሉም። የእጅ ጽሑፉን ብቻ ሳይሆን የሚጽፋቸው ጽሑፎችና ግጥሞች ይዘት ጭምር ነበር ብዙዎችን የሚስበው።
#በኋላ 12ኛ ክፍል ፈተናን ከመውሰዱ አስቀድሞ፥ የስዕል ትምህርትን ለመማርና መምህሩ የዘራበትን ዘር ለማፍራት ዝንባሌውን ተከትሎ በዘመኑ አዲስ አበባ የሥነ ጥበብ ትምህርት ቤት (አሁን አለ ሥነ ጥበብና ዲዛይን ትምህርት ቤት) አቀና። ትምህርት ቤቱን ለመቀላቀል ደጅ ጥናትና ምልልስ እንዲሁም ተማጽኖ አስፈልጎታል። በኋላም ተሳክቶለት ተማሪ ለመሆን በሚጠበቀው ፈተና አንድ ሺህ ከሚጠጉ ተወዳዳሪዎች መካከል ከ14 አላፊ ተማሪዎች አንዱ መሆን ቻለ።በ1971።
#በአንድ ወቅት በአራዳ ኤፍኤም አዲስ አራዳ የራድዮ ፕሮግራም ላይ ባደረገው ቆይታ፣ የዚያን የአምስት ዓመት የትምህርት ዘመን ሲያነሳ፥ በትምህርት ቤቱ የነበረው የ5 ዓመት ቆይታ ቀላል እንዳልነበር ያስታውሳል። ሌሊት ማረፊያ የሚያጣባቸው ቀናት ብዙ ናቸው። ምንም እንኳ ለአምስት ዓመታት እያንዳንዱ ቀን የአንድ ዓመት ያህል ከባድ የነበር ቢሆንም፥ እርሱ ግን ‘ቀኑን ጎበዝ መሆን ነበር የሚፈልገው’። እናም ቀኑን ጎብዞ ከባዱን ጊዜ በብልሃትና በጽናት ተወጣው። ትምህርቱን አጠናቅቆም በማዕረግ ተመረቀና እዚያው የተማረበት ትምህርት ቤት መምህር ሆኖ ተቀጠረ።
በተማረበት ትምህርት ቤት በወጣት መምህርነት ለአራት ዓመታት አገልግሏል። ከዚያ በኋላ፥ ወደ ሩሲያ ለከፍተኛ ትምህርት ተላከና ሞስኮ ከተመ። ‘ግራጫ’ ይለዋል፣ የሩስያን ፀሐይ አልባ ቀዝቃዛና ደመናማ የጨላለመ የዘመኑን ድባብ። በዙሪያው ውበትን ማሰስ የለመደ ዐይኑ በሞስኮ ያንን ሊያገኝ አልቻለም። እንዲያም ሆኖ የደከመለት ትምህርቱን ለመፈጸም ጽናትን በመምረጥ፥ ከስድስት ዓመት የሞስኮ ቆይታ በኋላ የከፍተኛ የሥነጥበብ ትምህርቱን በሚገባ አጠናቅቆ ወደ እናት ሀገሩ ኢትዮጵያ ተመለሰ።
ከሩስያ መልስ አስቀድሞ በመምህርነት ያገለግልበት በነበረው ሥነ -ጥበብ ትምህርት ቤት የማስተማር እድል አገኘ። በዚያም በመጀመሪያ በሥነ ጥበብ ታሪክ ከዚያም በንድፍ ጥናት መምህር ሆኖ ቆይቷል። በመምህርነት ብቻም አይደለ፥ በጊዜው ‘አርት ስኩል’ ይባል የነበረውን ይህን ትምህርት ቤት፣ ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋምነት ለማሳደግ ከ1990ዎቹ ጀምሮ ለዓመታት በዘለቀውና በተደረገው እልህ አስጨራሽ ትግል ውስጥ ከፊት ሆነው ሲያስተባብሩ ከነበሩት መካከል ሆኗል። በመጨረሻም ከምክትል ጠቅላይ ሚኒስቴር ቢሮ በተሰጠ የጥናት ውሳኔ ሥነ ጥበብ ትምህርት ቤቱ ወደ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተዛውሮ የከፍተኛ ትምህርት ተቋም ሲሆን ትልቁን ድርሻ ከተወጡት ጥቂት ግለሰቦች መካከል ፕሮፌሰር በቀለ መኮንን ተጠቃሽ ነው።
ትምህርት ቤቱ የዩኒቨርሲቲው አንድ አካል ክፍል ከሆነ በኋላ የመጀመሪያው ዳይሬክተር በመሆን ሠርቷል። በዚያም ወቅት የትምህርት ቤቱን ነባር ስርዓት የከፍተኛ ትምህርት ስርአት ቅርፅ ለማስያዝ በብርቱ ለፍቷል፣ አሳክቷልም። በ2009 ዓ.ም ገደማ የሥነጥበባት ኮሌጅ ሲመሠረት በድጋሚ የትምህርት ቤቱ ዳይሬክተር ሆኖ ከማገልገሉ ባሻገር፥ ትምህርት ቤቱ መጠሪያው ወደ አለ የሥነ ጥበብና ዲዛይን ትምህርት ቤት የተቀየረው የኮሌጁ ዲን ሆኖ ባገለገለበት ዘመን ነበር። ከዚያም ባሻገር አዲስና ተጨማሪ የፊልም ትምህርት ክፍል እንዲቋቋም ከፍተኛ ጥረት በማድረግ ትምህርት ክፍሉ እውን እንዲሆን አስችሏል። ከዚህም ባሻገር በማስተማርና በማማከር በርካታ ተማሪዎችን ያፈራ ብርቱ ባለሙያ ነው።
#ፕሮፌሰር በቀለ በብሉይ ወይም ክላሲክ አካዳሚ ትምህርቱን ጠንቅቆ የተማረ ይሁን እንጂ በዘመነኛ የሥነ ጥበብ እንቅስቃሴ በኢትዮጵያና በአፍሪካ ከሚጠቀሱ ባለሙያዎች አንዱ ነው። አዳዲስ ሙከራዎችና አሰሳዎችን በድፍረት ግን በኃላፊነት በማከናወን ሁሌም ፈር ቀዳጅና አዲስ መንገድ የሚያሳይ ከልቡ የፈጠራ ሰው ስለመሆኑም ብዙዎች ይመሰክራሉ፥ ከዚያም በላይ ሥራዎቹ ምስክሮቹ ናቸው።
#ፕሮፌሰር በቀለ የመጀመሪያ የሥዕል ኤግዚቢሽኑን ያቀረበው ከሀገር ውጭ ፊንላንድ፥ ‘ኮ’ፕዮ’ የሚባል ዩኒቨርሲቲ (Kuopio - በአሁኑ ምሥራቅ ፊንላንድ ዩኒቨርሲቲ) ነበር። ይህም በሞስኮ የሥነጥበባት የመጨረሻ ዓመት ተማሪ እያለ ሲሆን፣ ለዕይታ ያቀረባቸው ሥራዎቹም የተለያዩ አስቀድሞ በትምህርት ቤት ቆይታው ያዘጋጃቸው ናቸው።
ከዚያ በኋላ ለቁጥር በርካታ፣ ለዓይነት ብዙ፣ ለዐይን ውብና አስደማሚ የሆኑ ሥራዎችን ያለማቋረጠ ለበርካታ ዓመታት ሲያቀርብ ቆይቷል። ከስዕል ኤግዚቢሽን እስከ አደባባይ ሐውልቶችና ዓለም አቀፍ መድረኮች፥ በቀለ መኮንን የሚለው ስም እንግዳ ሆኖ አያውቅም።
#በ1996 ዓ.ም ያቀረበው ‘እንቆቅልሽ’ የተሰኘ የ‘ኢንስታሌሽን ጥበብ’ ትርዒቱ ዘይቤያዊ (Methaphorical) ትርጉም የያዘና አሁንም ድረስ አነጋጋሪ ሆኖ የቆየ ሥራ አንዱ ተጠቃሽ ነው። በ2000 ዓ.ም ‘እድልና ምርጫ’ የሚል ‘ክሪቲካል’ ትርዒቱን አቅርቦ ተመልካቹን አስደምሟል። በ2010 ዓ.ም ‘ባሩድና ብርጉድ’ ሲል የሰየመው አነጋጋሪና አወያይ ኤግዚቢሽኑ፥ ተመልካቹ ስለ ሥነጥበብ ያለውን አመለካከት ደጋግሞ እንዲፈትሽ ያስገደደ ነበር።
በ2016 ዓ.ም በኢትዮጵያውያን የሕይወት ዘይቤ ላይ ትልቅ ጥያቄ አንስቶ ያወያየውንና እስከ አሁንም የሚያወያየውን “ግሉተን ፍሪ-ደም” ወይም ‘ጤፍና ነፃነት’ የተሰኘውን ልዩ ትርዒት አቅርቦ የሥነ ጥበብ ተመልካቾችን ማስደነቁና ማነጋገሩን ቀጠለበት።
ከ25 ዓመታት በላይ እነዚህን የፈጠራ ሥራዎቹን በሀገር ውስጥ እና በውጭ ሀገር በተለያዩ መድረኮች ሲያሳይ ቆይቷል። በአፍሪካ፣ በአውሮፓ እና በአሜሪካ፣ በተለያዩ ሙዚየሞች ሥራዎቹን አቅርቧል፣ ሐሳብና ዕይታውን አስደምጧል። ሀገሩን አልፎም አኅጉሩን አፍሪካን በዓለም መድረክ በዘርፉ በኩራት እንዲቆሙም ምክንያት ሆኗል።
#በቅርብ ማለትም ባለፈው 2017 ዓ.ም፥ በኢጣሊያ ቱሪን ከተማ ሮያል ፓላስ ሙዚየም ተጋብዞ ‘ዘ ስሞኪንግ ቴብል’ ወይም ‘የሚጤሰው ጠረጴዛ’ የተሰኘ ፀረ ቅኝ ግዛት ይዘት ያለው ዘመነኛ የሥነ ጥበብ ሥራ በመፍጠር ለዕይታ አቅርቧል። ይህም ከፍተኛ እድናቆትን ያስገኘለት ብሎም ሐሳቡን ያስደመጠበት አውድ መሆን ችሏል።
#መሥራት እንጂ ይህን ሠራሁ ብሎ መናገርን የማያዘወትረው ፕሮፌሰር በቀለ፣ እንዲህ ካሉ አውደ ርዕዮች ባሻገር በቀራጺነቱ የተጠበበባቸው ሥራዎችም እጅግ በርካታ ናቸው። ከቅርብ ዓመታት ወዲህ የሠራቸውን በማማከር የተሳተፈባቸውን ብቻ ለመጥቀስ፥ በሙሉ ነሃስ የተሠራው የቀዳማይ ኃይለሥላሴ ኪነ ሀውልትን ጨምሮ፥ አብርኆት የሕዝብ ቤተመጻሕፍት ደጃፍ የሚገኘው ኪነ ሀውልት (ከነሐስ ቀልጦ የተሠራው ሕፃን)፣ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ዋና መሥሪያ ቤት ያሠራው ሕንጻ ጋር የሚገኘው የባንኩን ዓላማና ርዕይ የሚያሳየው ግዙፍ ኪነ ሀውልት (ሀብት ካለ በሰማይ መንገድ አለ) እጅግ ጥቂቶቹ ናቸው።
ታድያ ለእነዚህና ለበርካታ ሥራዎቹ ሽልማቶችና እውቅናዎች ተበርክተዉለታል። ከእነዚያም መካከል በ1990 ዓ.ም የቺካጎ አርቲስቶች ዓለም አቀፍ ሽልማትን ያሸነፈ ብቸኛው አፍሪካዊ የስነ ጥበብ ባለሙያ መሆን ችሏል። እ.ኤ.አ. በ2006 በአሜሪካ ኒው-ዮርክ ውስጥ የIIE ፕሮግራም የሆነውን የ’Scholar Rescue Fund’ ሲቀበል የመጀመሪያው የሥነ ጥበብ ሰው ነበር። በዚያው ዓመት በባልቲሞር ሜሪላንድ ውስጥ በተጋባዥ ሠዓሊነት በበሜሪላንድ የአርት ኮሌጅ (MICA-Maryland institute college of Art) ለስምንት ወራት ቆይታ አድርጓል።
#ፕሮፌሰር በቀለ የኢትዮጵያ ሚሌኒየም ዓርማ ነዳፊ ሲሆን በመላ ሀገሪቱ በርካታ ኪነ ሀውልቶችን ነድፏል፣ አቅዷል፣ አማክሯል፣ መርቷል፣ ሠርቷል። በርካታ የመጻሕፍት ሽፋኖችንና የውስጥ ምስሎችን አዘጋጅቷል። በሀገር እና በዓለም አቀፍ የሥነጥበብ እና የሥነ ሕንፃ የውድድር መድረኮች ላይ በከፍተኛ ዳኝነት አገልግሏል። ከስነጥበቡ ማኅበረሰብ ውስጥ ደግሞ በኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ መደበኛ አባል ነው።
#ከዚህም በላይ ከእለት እለት የማስተማር ተግባሩ ጎን ለጎን በቅርቡ በተባበሩት መንግሥታት ፕሮጀክት ስር ነባሩ የአፍሪካ አዳራሽና የሥነ ጥበብ ሥራዎቹ እድሳት ውስጥ ባለሞያ፣ አማካሪና ተቆጣጣሪ በመሆን የተሳካ ሙያዊ ተልዕኮ ፈፅሟል። በአሁኑ ወቅትም በአለ ሥነጥበብ እና ዲዛይን ትምህርት ቤት የቅድመ እና ድኅረ ምረቃ ፕሮግራም ፕሮፌሰር ሲሆን፣ የዘመናዊ ሥነጥበብ ሙዚየም ገብረ ክርስቶስ ማዕከልንም በመምራት ላይ ይገኛል።
#ኅዳር 4 ቀን 2018 ዓ.ም የአለ የሥነጥበብና ዲዛይን ትምህርት ቤት የቀድሞ ተማሪዎች በትምህርት ቤቱ የአክብሮትና የምስጋና ፕሮግራም አድርገዉለታል። ተማሪዎቹ ያንን ያደረጉት ፕሮፌሰር በቀለ በጀርመን ሀገር ፍራንክፈርት ከተማ ከሚገኝው የሥነጥበብ ዩንቨርሲቲ ጋር ከዓመታት በፊት የተጀመረውን የኹለትዮሽ ግንኙነት ዳር በማድረስ ላደረገው ታላቅ ተግባር እና የትምህርት ቤቱን ዳግም ትንሳኤ ለማሳካት ድልድይ በመሆኑ በማመስገን ነው።
አሁን ታድያ ይህና ያልተነገረ እጅግ በርካታ፣ ውብና አስደናቂ፣ ገና ያልተተነተነና ዐይን የሚሻ ሥራን የሠራ ሰው ነው፥ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ አለ የሥነጥበብና ዲዛይን ትምህርት ቤት የመጀመርያው ሙሉ ፕሮፌሰር ማዕረግ የተሰጠው።
#ምንአሉ ?
ይህንን ዜና በደስታ በማኅበራዊ ገጾቻቸው ካጋሪት መካከል ጋዜጠኛ #ቴዎድሮስተክለአረጋይ እንዲህ አለ፥
“አንዳንድ ጊዜ ማዕረግም፣ ሹመትም፣ ሽልማትም በተለያዩ ምክንያትና አጋጣሚዎች ያልተገባ ሰው እጅ ውስጥ ሊገቡ ይችላሉ። ይህ ይበልጡን በሀገራችን፣ በዓለምም ላይ ታይቷል። ለፕሮፌሰር በቀለ መኮንን ዓይነቱ ደግሞ እንዲህ ግጥም ያለ ፣ በልኩ የተሰፋ ይሆናል። የበቄ ፕሮፌሰርነት በሥነ ጥበብ ዘርፍ የተሰጠ የመጀመሪያው ቢሆንም የሰውየው የበቀለ ብቻ አይደለም። የመጭው ትውልድ ሁሉ ነው። የሥነ ጥበብነት ብቻ ሳይሆን የመቻል ፕሮፌሰርነት ነው። ከእንግዲህ ለአንድ ጥበበኛ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሙሉ ፕሮፌሰርነት ማዕረግ መሰጠት እንደሚችል ማሳያው፣ ማመላከቻው፣ ዳገቱ፣ ምልክቱ ነው፥ በቀለ መኮንን። ያሉትና የመጭዎቹ የሥነጥበብ ልሂቃን ተስፋና ብርታት ነው። እንደሚቻል ማሳያውም፣ ማረጋገጫውም ሆኗል። ይህ ለሥነጥበቡ ብቻም ሳይሆን ለሙዚቃውም ፣ ለትያትሩም ነው።”
የሙያ አጋሩንናበአለ የሥነ ጥበብ እና ዲዛይን ትምህርት ቤት ዲን #ሠዓሊአገኘሁአዳነ በበኩሉ፥ “የቤት ሰው፣ መምህር፣ ባልደረባ፣ የሞያ አባት… ከፍ ሲል፣ ሲከብር፣ ድካሙ ፍሬ ሲያፈራ ወዘተ. ልብ ይሞላል። በቀለ መኮንን ንጉሡ ባለግዙፍ ሰብዕና፣ ከሰው ፊት የሚያቀረቡት፣ የሚያኮራ፣ ጥንቅቅ ያለ ሙያተኛ፣ በጥረቱ ከጉልበተኞች ቅሚያና ንጥቂያ፣ ከሰሜነኛው ንፍቀ ክበብ (global north) በር ጠባቂነት በጥበብ ሾልኮ በርካታ ዓለማቀፍ መድረኮችን የተጋራ፣ ረብ ያለው ተግባር እየፈጸመ ያለ ሰው የሚሠራበት ተቋም አዲስ አበባ ዮኒቨርስቲ የሙሉ ፕሮፌሰርነት ማዕረግ ሰጥቶታል። የአለ የሥነጥበብና ዲዛይን ትምህርት ቤት የመጀመርያው ሙሉ ፕሮፌሰርሽፕ ማዕረግ መሆኑ ነው።” ሲል አያይዞ የእንኳን ደስ አለህ መልዕክቱን እስተላልፏል። #ደራሲእንዳለጌታከበደ (ፒኤችዲ) “አሁን የሆንከውን ለመሆን፣ አንተው ራስህ የጻፍከውን ግጥም ኖሮ መገኘትን ይጠይቃል።” ሲል መግቢያ አኑሮ ባጋራውና ራሱ ፕሮፌሰር በቀለ መኮንን በጻፈው ‘ቼ በለው’ በተሰኘው ግጥም እናብቃ፥
ቼ በለው!
ሕይወት ጎዳናው ገጹ ሲለወጥ
በጭነት ታክቶ ጀርባው ሲመለጥ
የእንቅፋት አጽሙ ቋጥኙ ሲገጥ
ሸክም ዘንቦበት ትቢያው ሲላቆጥ
ሲሆን ድጥ በድጥ
ሾህ ጭቃ ቅይጥ
ልብህ አይደንግጥ።
በምኞት ቅዥት በስጋት ርዶ
አይፍረስ ግንቡ ወኔህ ተንዶ
ከቆመው ቆመህ ከንፈር ከመምጠጥ
በተስፋ ፈረስ በልጓም ሸምጥጥ።
አያረጅ የለም አይለዋወጥ
ነገን ተማምነህ በመጓዝ ቁረጥ…
ከሩቅ አልመህ ቅርብ አትርመጥመጥ
ሰግተህ ከምትቆም ስትጋልብ ፍረጥ።
#መምህሩጋሽወርቁ ስለ ፕሮፌሰር በቀለ
መምህር ወርቁ ጎሹ የፕሮፌሰር በቀለ መኮንን አስተማሪ ሲሆኑ የ85 ዓመት ሰውም ናቸው። በቀለ ከወጣትነቱ አንስቶ ህልሙን ለማሳካት ታላቅ ጥረት የሚያደርግ ተማሪዬ ነው ሲሉ በኩራት ምስክርነት ይሰጣሉ። መምህር ወርቁ ጎሹ ቀራጺ በቀለ ከሰዎች ጋር የመግባባት ክህሎትን የታደለ የሚወደውን ሙያ እየሠራ ያለ ብቃት ያለው የሥነ ጥበብ ባለሙያ ነው ሲሉ ይገልጹታል።
ጋሽ ወርቁ 30 ዓመታት አስተምረዋል። በቀለን ሲገልጹት የሚደነቅና የሚከበር ይሉታል። በራሳቸው ጥረት ካደጉት ተርታ ይመድቡታል።
ጋሽ ወርቁ ወደ ኃላ መለስ ብለው የፕሮፌሰር በቀለን የትምህርት አቀባበል ሲያጤኑ የቀን የሌት ጥረት የሚያደርግና የልፋቱን ያገኘ በሚል ያስረዳሉ። ተሰጥዖም የሚታይ ነው ይላሉ።
ዛሬ ፕሮፌሰር መሆኑ ለአገር ትልቅ ኩራት መሆኑንም ነግረውናል።
" የበቀለ ፕሮፌሰር መሆን ለእኔ ብቻ ሳይሆን ለአገር ኩራት ነው። እኔ እንደ አስተማሪው ይህን የምሥራች ስሰማ ደስታዬ ያይላል።እንኳን ደስ ያለህ ልለውም እወዳለሁ። "ሲሉ ለተወዳጅ ሚድያ ምስክርነት ሰጥተዋል።
በቀለ መኮንን፤
በብሔራዊ ትእምርት ፍለጋ ውስጥ
#በተባባሪፕሮፌሰርቴዎድሮስገብሬ
I
ከብረት እስከ ጨርቅ በደረሱ ትይዩ ተቃራኒዎች መካከል ሲያመላልሰን የከረመው በቀለ መኮንን፣ ጥቁር ጤፍ ፈጭቶ--ጥቁር ጤፍ አቡክቶ “በጋገራቸው” ኪነቶች አማካይነት ሊፈትነን “ጤፍና ነጻነት” የሚል ርእስ በሰጠው አዲስ ትርኢት ተገልጧል፡፡ “ጤፍ” እና “ነጻነት”? ጤፍ ገቢር ነው፡፡ ነጻነት ደግሞ ኀልዮ፡፡ ጤፍ ይሰፈራል፤ ይፈጫል፤ ይቦካል፤ ይጋገራል፡፡ ነጻነት ግን በኅሊና ይነደፋል፡፡ ጤፍ እና ነጻነት በነገረ ፍጥረታቸው አይገናኙም፡፡ 'እናስ በምን ተጠየቅ ተዛምደው በአንድ ርእስ ውስጥ በ“እና” ተዳሩ?' የሚል ጠያቂ ከመጣ ምላሹን የሚያገኘው ከትርኢቱ ዐውድ ይሆናል፡፡
በቀለ በትርኢት መግለጫዎቹ በገሀድ እንደሚጠቁመን በአዳዲስ ሥራዎቹ ውስጥ ረቂቁ “ነጻነት” በግዙፉ ጋሻ ውስጥ አድሮ ተጨባጭ ሆኗል፡፡ በእርግጥ ጋሻ የሚመስሉ “እብጠቶች” በበቀለ ዕይታዊ መድበለ ቃላት ውስጥ የሰርክ ጉዳዮች ናቸው፡፡ በቀደሙት ትርኢቶች ውስጥ ጋሻዎች አንድም ቅርጽ ከቅርጽ ተጋጭተው ለሚፈጥሩት “ግብታዊ” ፍቺ ሲባል ይመላለሳሉ፤ አንድም ደግሞ የማረሻን የገነነ ወንዴነት ማስከኛ ሆነው በሚዛን ጠባቂነት (as a feminine energy) ይመጣሉ፡፡ በ“ጤፍና ነጻነት” ነጻነት በጋሻ ውስጥ በማደሩ፣ ጋሻ ከቀደመ ግብሩ የተለየ አዲስና ቋሚ ሚናና ግብር ይዟል ማለት እንችላለን፡፡ አዲስ ግብር ለመያዙ ምስክሩ ይህ ብቻ አይደለም፡፡ በትርኢቱ ውስጥ የሚገጥሙን ጋሻዎች በሙሉ በጤፍ ዱቄት የተገነቡ (የተለሰኑ) ናቸው፡፡ የጋሻዎቹ በጤፍ ዱቄት መገንባት አንድም፣ በትእምርቶቹ መካከል የባሕርይ መጋራት እንዲፈጠር፤ አንድም በኪነቱ ውስጥ ጥንድ ምናብ--ድርብ አስተማስሎ (double representation) እንዲከሰት ዕድል ሰጥቷል፡፡ የጉዳዮች በአንድ ወደተሸረቡ መንታ ትእምርትነት ማደግ ተመልካች ሐሳቡን የሚያሰላበትን፣ ትችቱን የሚያፍታታበትን ምቹ የመፈከሪያ ዐውድ እንዲያገኝ አስችሎታል፡፡
ጋሻ የነጻነት እና የአርበኝነት ማኅደር ነው፡፡ (ይህ ዓይነቱ የጋሻ ፍቺ በተገኘበት ባህል ውስጥ ጭምር ይታወቃል፡፡) ቆየት አድርጌ በስፋት እንደማሳየው ጤፍ በፈንታው የ“ኢትዮጵያ” እና “የኢትዮጵያዊነት” ብሔራዊ ትእምርት ነው፡፡ በዚህ ዐውድ የብሔራዊ ትእምርት ፋይዳ አንድም፣ በነጻነት፣ በአገር እና በብሔራዊ ምንትነት መካከል ያለውን ረቂት ተራክቦና ውስብስብ ተጻምሮ ተጨባጭ ማድረግ ነው፡፡ አንድም ደግሞ ተራክቦውን--ተጻምሮውን ጠብቆ ለማኖር ዜጎች በአርበኝነት መንፈስ የሚከፍሉትን የላብና የደም መስዋዕትነት ማመልከት ነው ማለት እንችላለን፡፡ (በ“Gluten-free-dom II” እንጀራ የጠመጠመ ጋሻ በአናታቸው የደፉ፣ በትኩስ የአመድ ደለል ላይ/ውስጥ የቆሙ ሰባት እናቶች እንዲህ ላለው አንድምታ አስረጂዎች ይሆኑናል፡፡)
II
ብሔራዊ ትእምርቶች የብሔራዊ ምንትነት ግላጼዎች (identity expressions) ናቸው፡፡ የምንትነቱ ሥሪት (identity construction) በተረኮቹና በትእምርቶቹ ጥራትና ጥንካሬ ላይ ይወሰናል፡፡ ግላጼዎቹ እና ሥሪቱ የሚተጋገዙ ብቻ ሳይሆን የሚተካኩ ጉዳዮች ጭምር ናቸው፡፡ ያንዱ መድከም ሌላውን ያጎድላል፡፡ ያንዱ መዛል ሌላውን ያፈርሳል፡፡ የብሔራዊ ትእምርት ቀረጻ ብሔራዊ-ጥበባዊ ተልእኮ ነው፡፡ የአንድ ሕዝብ ብሔራዊ ምንትነት በአንጻራዊነት ለዘመናት ጸንቶ ይዘልቅ ዘንድ ተረኮች (ቃላዊ፣ ዕይታዊ፣ ትውናዊ፣ ወዘተ. ተረኮች) እና ትእምርቶች በጥንቃቄ መመረጥና መቀናበር፣ በየጊዜው እየተመረመሩ መታረምና መከለስ ይኖርባቸዋል፡፡ ብሔራዊ ምንትነት በዐቢይነት የውክልና ጉዳይ ነው፡፡ በአንድ አገር ውስጥ እያሉ እንደሌሉ የተቆጠሩ ወገኖች፣ ቸል የተባሉ ሰብአዊ ዕሤቶች፤ አቅም ባገኙ፣ የኃይል ሚዛን በለወጡ ጊዜ በነባር ተረኮች እና ትእምርቶች የተሸመነውን ብሔራዊ ምንትነት እስከ መሻር፣ አፍርሶ እንደ አዲስ እስከመሥራት የሚያደርስ ጥያቄ ያነሳሉ፡፡ ይህ ሲከሰት የአገር ግንባታ ሂደት ይስተጓጎላል፤ ማኅበራዊ ውጥረት ይነግሣል፡፡ (የዛሬዋ ኢትዮጵያ ለዚህ ዓይነቱ እውነታ አብነታችን ናት፡፡) በመሆኑም ብሔራዊ ትእምርት ቢያንስ ቢያንስ ረጅም የታሪክ ዘመንን፣ ሰፊ መልክአ ምድርን እና ገሀድ የወጡ የማኅበረሰብ ክፍሎችን እና ዕሤቶችን ሊያካልል ይገባል፡፡ ብሔራዊ ትእምርት ከውክልናው ፈርጀ ብዙነት ባሻገር በኪነት ከፍታው እና በኀልዮ ጥራቱም ተለይቶ መታወቅ አለበት፡፡ ጥቅል በሆነ አነጋገር፣ ብሔራዊ ትእምርት ጥልቅ በሆነ ጊዜ ውስጥ፣ ጽኑእ በሆነ መሠረት ላይ የሚታነጽ በነባርና በአዳዲስ ዕሤቶች ትብብር የሚሸመን ዐውራ ምስል ነው፡፡
እንደ ኢትዮጵያ ላለ ኅብረ ባህላዊ አገር ብሔራዊ ትእምርት በትግግዝ የሚፈጸም ብሔራዊ--ኪናዊ ተልእኮ ነው፡፡ ብሔራዊ ትእምርት እርስ በርስ ሊናበቡና ሊከታተሉ በሚችሉ በግለሰብ፣ በቡድን፣ በትውልድ በሚፈጠሩ ገባር ምናቦች ትግግዝ በዘመናት ሂደት ምልዓት ላይ የሚደርስ ዐውራ ትእምርት ነው፡፡ እንዲህ ዓይነቱን ኪናዊ ትግግዝ--የምናብ ተናባቢነትና የምስል ተከታታይነት--በተጨባጭ ለማሳየት “ጤፍና ነጻነት”ን በሁለት መንገዶች ማንጸር እንችላለን፡፡ ቀዳሚው መንገድ ይህንን ትርኢት ከበቀለ መኮንን ነባር ትርኢቶች ጋራ እያመሳከሩ መፈከር ሲሆን፤ ተከታዩ ደግሞ በየትኛውም የኪነት ዘርፍ ካሉ ዘመነኞቹ ጋራ--ለምሳሌ ከአዳም ረታ ጋራ--እያናበቡ ማስተሳሰር ነው፡፡ የበቀለ መኮንንን ዕይታዊ ጥበብ ከአዳም ረታ ቃላዊ ኪነት አናብቦ በብሔራዊ ትእምርትነት ለማስላት በቂ ምክንያቶች አሉ፡፡ ለዛሬው ትርኢት የነፍስ ያህል የሆነውን ዐውራ መባያ[1]--ጤፍን በበቀለ የአከያየን ልማድ ውስጥ ከገነነው፣ ከማረሻ ጋራ አስተሳስሮ ለማሰብም እንዲሁ፡፡ ከምክንያቶቹ ውስጥ መሠረታዊዎቹ፡- አንደኛ፣ የዐውድ ተዛማጅነት፤ ሁለተኛ፣ የኀልዮ (የጭብጥ) ተከታታይነት፤ ሦስተኛ፣ የቅኝት ወይንም (የርእዮተ ዓለም) ተወራራሽነት፤ አራተኛ፣ የጊዜ ጥልቀት (የነገረ ፍጥረት ብሉይነት)፤ አምስተኛ፣ ሥነ ልሳናዊ ተዛማችነት ናቸው፡፡
“ማረሻ” የግብርና ማምረቻ መሣሪያ፣ “ጤፍ” ደግሞ የግብርና ምርት በመሆናቸው በተፈጥሮ የቅደም-ተከተል ዝምድና አላቸው፡፡ (ተፈጥሯዊው ቅደም ተከተል በጉዳዮቹ መካከል አለ ያልነውን የጭብጥ ተከታታይነት እና የትእምርት ተጋጋዥነት ተጨባጭ ያደርግልናል፡፡) የማምረቻ መሣሪያው (ማረሻ)፣ የአምራቹ (ገበሬ) እና የምርቱ (ጤፍ) ተፈጥሯዊ የተራክቦ ዐውድ ገጠር ነው፡፡ ጤፍ እና ማረሻ ከ85 ከመቶ በላይ ኢትዮጵያዊ ይኖርበታል የሚባለውን፤ ዳሩ ግን በአገሪቱ ፖለቲካዊ፣ ማኅበራዊ እና ምጣኔ ሀብታዊ እንቅስቃሴ ውስጥ ተገቢ ሥፍራ የተነፈገውን ወገን በቀጥታ ይመለከታሉ፡፡ ከያኒው ለተገፉ፣ ሥፍራ ለተነፈጉ ብሔራዊ ጉዳዮች ማድላቱ የትእምርቶቹን ምርጫ ተገቢነት ከማረጋገጡ ባሻገር ቅኝቱን ርእዮተ ዓለማዊ ያደርገዋል፤ (“history from below” እንደሚባለው)፡፡ ገጠርን አትኩሮ፣ ነባር የግብርና መሣሪያንና ጥንታዊ ምርትን (ማረሻንና ጤፍን) ከዚያው ዐውድ መልምሎ በምናብ ማጥለቁ፣ በምስል ማበልጸጉ እና በኀልዮ ማራቀቁ ብዙኃኑን የሚወክል፣ ዘመናትን የሚዋጅ ጽኑእ ብሔራዊ ትእምርት ለመቅረጽ ዕድል የሚሰጥ ይመስለኛል፡፡
የጤፍ ነገረ ኪን እና ፖለቲካም (the poetics and politics of teff) በቅኝት ከዚህ የሚለይ አይመስለኝም፡፡ ጤፍ በመጠን በአነስተኛነቱ “ዝነኛ” ነው፡፡ ለምሳሌ፣ አንድ የስንዴ ቅንጣት በአማካይ ከአንድ መቶ ሃምሳ የጤፍ ቅንጣቶች ጋራ እኩል እንደሆነ ይገመታል፡፡ ይህ ደግሞ “ከትውልድ ሥፍራው” አልፎ በዓለም ካሉ የእኽል ዝርያዎች በሙሉ በመጠን ትንሹ ያደርገዋል፡፡ በደስታ ተክለ ወልድ መዝገበ ቃላት ይህ የእኽል ዘር በተከታዩ መንገድ ተበይኖ እንመለከታለን፤ “ጤፍ፤ የታናሽ እኽል ስም፤ የሣር ዐይነት ሙርዬ የሚመስል፡፡ (ተረት)፤ ሳይቸግር ጤፍ ብድር” (19962፡ 675)፡፡[2] በዓለም ምግብ ድርጅት ገጽ ላይ ሰፍሮ እንደምናነበው፣ ጤፍ ከኢትዮጵያ ውጪ ባሉ አገራት፣ ለምሳሌ በደቡብ አፍሪካ እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ ከከብቶች ቀለብነት ባለፈ የአፈር መሸርሸርንና የውሃ ብክነትን ለመቀነስ ታስቦ የሚለማ “ተራ ሣር” ነበር፡፡[3] ተወዳጅ ነው በሚባልባት እናት አገሩም ቢሆን በመጠን ማነሱን ታክከው የሚቀርቡ ንጽጽሮች አጓጉልነት አላጣቸውም፡፡ ለአብነት፣ “ከመጤፍ አልቆጠረኝም” እና “ሰው ጤፉ” የሚሉ አገላለጾች በደረጃ ማነስን በገሀድ ያውጃሉ፡፡
ጤፍ በጄኔቲካዊ አወቃቀሩ እጅግ የተወሳሰበ፣ በጾታ ቅንብሩ የተደባለቀ (ፈናፍንት)፣ በምግብ ይዘቱ የበለጸገ የእኽል ዓይነት እንደሆነ የአዝርእት ባለሙያዎች ያስረዳሉ (ሰይፉ 1997)[4]፡፡ ሰይፉ ከተማ በመስኩ ላይ የተካሄዱ ምርምሮችን በከለሱበት ጽሑፋቸው እንደሚያስረዱን፣ የጤፍን የትውልድ ቦታ በእርግጠኝነት መናገር ቢከብድም፣ ጄኔቲካዊ ብዝኃነቱን በማጤን ኢትዮጵያ እናት ምድሩ ልትሆን እንደምትችል መገመት አስቸጋሪ አይሆንም፤ “[T]he genetic diversity for teff exists nowhere in the world except in Ethiopia, indicates that tef originated and was domesticated in Ethiopia” (12)፡፡ ጤፍ በዓለም አቀፍ ደረጃ እጅግ ጥንታዊ ከሚባሉ ጥቂት የእኽል ዘሮች መካከል አንዱ ነው፡፡ በዚህ የእኽል ዘር ላይ ከተካሄዱ ምርምሮች መካከል ብዙዎቹ፣ Nicolai Vavilovን (1951)[5] መሠረት በማድረግ፣ ቅድመ ክርስቶስ ከ4000–1000 በኢትዮጵያ ውስጥ እንደበቀለና ተስፋፍቶ እንደለመደ ይገምታሉ፡፡ እንደ ጤፉ ሁሉ፣ “ኢትዮጵያዊው” ማረሻ፣ ከዕድሜው ጥንትነት ባለፈ ልደትና ዕድገቱም እዚሁ መሆኑን የሚያመላክቱ ምርምሮች አሉ፤ ለምሳሌ፣ Hubert Cochet ኢትዮጵያውያን ገበሬዎች በማረሻ ለ2000 ዓመታት እንዳረሱ ይጠቁማል (2011፡ 31)፡፡[6]
በኢትዮጵያ ውስጥ ከሦስት ሺህ በላይ ዘመናትን ያስቆጠረው፣ ከአገሪቱ ሕዝብ መካከል 70 ከመቶው በእንጀራ መልክ ይመገበዋል ተብሎ የሚገመተው ጤፍ (ታደሠ 2017፡ 50) በሦስቱ ዐበይት የሥነ ልሳን ቡድኖች ተቀራራቢ ስያሜም አለው፡፡ በአማርኛ “ጤፍ”፣ በኦሮምኛ “tafi” በትግሪኛ “ጣፍ”፡፡ በቀለም ስርጭትም ረገድ ወተት ከመሰለ ነጭ (ማኛ) አንስቶ እስከ ጥቁር ድረስ የሚዘልቁ አራትና አምስት ቀለማትን ያቅፋል (አዳም በሁሉም ቀለሞች የሚጫወት ሲሆን የበቀለ ምርጫ ጥቁሩ ነው)፡፡ እንዲህ ያለው የባሕርይ ውስብስብነት፣ የጾታ መንታነት፣ ኅብረ ቀለማዊነት ጤፍን--በአዳም ረታ ጥበበ ቃላት እና በበቀለ ዕይታዊ ጥበብ--ውስጥ ለብሔራዊ ትእምርትነት የተመቸ መባያ አድርጎታል፡፡ “ማረሻ” በበኩሉ ኢትዮጵያውያን የወል ምንትነታቸውን ከሚቀርጹባቸው ብሉይ ዕሤቶች መካከል አንደኛው ነው፡፡ የወልነቱን በዐበይቱ የኢትዮጵያ ቋንቋዎች ውስጥ ባለው የስያሜ ተወራራሽነት መረዳቱ አያሰቸግርም (የአማርኛው “ማረሻ”-- በግእዝ “ማሕረስ”፣ በኦሮምኛ “maarashaa”፣ በትግርኛ “ማሕረሻ” የሚሉ አቻዎች አሉት)፡፡ ብሉይ ነው ስል አንድም፣ የዘፍጥረቱን ጥንታዊነት፤ አንድም፣ የጊዜ ጥልቀቱን ታክኮ የሚመሠረተውን ባህል ጽኑእነት ማመልከቴ ነው፡፡ በተፈጥሮው ቀጥ ያለው፣ የተሳለውና የሾለው ማረሻ፣ በበቀለ ትርኢቶች ውስጥ በከያኒው ፈቃድ፣ ፍላጎትና እጅ መዋቅሩ ተናግቶ፣ “ተፈጥሮው” ተዛብቶ ልክ እንደ ጤፍ ወደ ፈናፍንትነት ተቀይሯል፡፡ የበቀለ ማረሻዎች መዋቅር መናጋት የአድሏዊው የተባዕትነት ሥርዓት ፈርሶ በአዲስ ተምኔታዊ ሥርዓት የመተካቱ አምሳያ ነው፡፡ ከዚህ ሥርዓት ውስጥ ነው እንግዲህ ከያኒው አዳዲስና ነባር ዕሤቶች ተዳርተው የሚሰናኙበትን ብሔራዊ ትእምርት ለመፍጠር የሚታገለው፡፡[7]
ጤፍ እና ማረሻ ኢትዮጵያውያን ጥልቅ ከሆነ ጊዜ፣ የጋራ ታሪካቸውን፣ ርእዮታቸውንና ንጽረታቸውን የሚጠልቁባቸው፤ ሩቅ ከሚባል ትናንት የወል ልቡናቸውንና ምንትነታቸውን የሚያደሩባቸው “ቁሳዊ” ዕሤቶች ናቸው፡፡ ቤኔዲክት አንደርሰን፣ “It is the magic of nationalism to turn chance into destiny” (1983፡ 12)[8] እንዳለው ዕጣ ፈንታቸው ጭምር ተጠላልፎ የተሰናኘባቸው የወል ዕሤቶች፡፡ ማን ከዕጣው ማምለጥ ይቻለዋል? እንደሚታወቀው እንዲህ ያለ ዕሤት በጥልቅ ጊዜ እና በጽኑእ መሠረት ላይ የሚቆም አገር ለማነጽ ምቹ ዕድል ይፈጥራል፡፡ በእርግጥ አንድ ማኅበር በጽናት ይቆም ዘንድ ዕጣውን ከቋጠረበት ሩቅ ትናንት በተጨማሪ፣ በገነነ “የሕዝብ ማኅበራዊ ልቡና” ነገውን የሚዋጅበት የጋራ ስኬት እንደሚያስፈልገው አሌ አይባልም፡፡ ለዚህ ዓይነቱ ስኬት ጤፍ እንግዳ አይመስለኝም፡፡ ትናንት፣ ጤፍን ለሰው ልጅ ምግብነት በማዋል ረገድ ኢትዮጵያ ከዓለም ብቸኛ አገር ነበረች፡፡ ዛሬ፣ በተለይ በአውሮፓና በሰሜን አሜሪካ በሚኖሩ፣ እንጀራን መለያቸው ባደረጉ በ“ነባሬ ባዕድ”[9] (diaspora) ኢትዮጵያውያን በሚተዳደሩ ምግብ ቤቶች አማካይነት ዝናን ያተረፈው ይህ የእኽል ዘር የኢትዮጵያን ድንበር ተሻግሯል፡፡ በጣዕሙ፣ በምግብ ይዘቱና ለጤና ባለው ጠቀሜታ ከተመጋቢው እኩል በሥነ ምግብ ተመራማሪዎች ዘንድ ተወዳጅ የሆነው ጤፍ በትልልቆቹ የዓለም የመገናኛ ብዙኋን ሳይቀር (ለምሳሌ፣ በBBC, VoA, The Washington Post, The Guardian, The New York Times, ወዘተ.) “the next ‘super grain’ of the World” የሚል መወድስ ወርዶለታል፡፡ ይህንን ዝና ተከትሎ ሊመጣ የሚችለው ማኅበራዊ ከፍታ እና ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ--(as a national branding) ብሔራዊ ክብርና ኩራትን የመፍጠር አቅም አለው፡፡ የጤፍ ታሪካዊ፣ ባህላዊ እና ማኅበረ-ኢኮኖሚያዊ ፋይዳው አንድም በመከባበር ላይ የተመሠረተ አንድነትን ለመፍጠር የሚያግዝ፤ አንድም በጎሣ፣ በሃይማኖት እና በቋንቋ ምክንያቶች የተፈረቀቀውን ብሔራዊ ልቡና (the national psyche) ለማከም የሚያስችል ዕድል እመስጠቱ ላይ ነው፡፡[10]
III
ትኩረታችንን ወደ ዛሬው ትርኢት እንመልስ፡፡ “ጤፍና ነጻነት”፡፡ ጤፍ የ“ኢትዮጵያ” እና “የኢትዮጵያዊነት” ብሔራዊ ትእምርት፤ ጋሻ በበኩሉ የነጻነት እና የአርበኝነት ማኅደር መሆኑን በመግቢያዬ አመልክቻለሁ፡፡ እንዲህ ያለው የጋሻ ትርጉም ህልው በሆነበት ባህል ውስጥ ጭምር ታውቆ የሚሠራበት ነው፡፡ በትርኢቱ ውስጥ ከቀረቡት ሥራዎች ብዙዎቹ ከጤፍ እና ከጋሻ ተራክቦ የተገኙ ናቸው፡፡ ይህ ማለት ግን ሁለቱ ጉዳዮች በሁሉም ትዕይንቶች ውስጥ እኩል ሥፍራ አላቸው ማለት አይደለም፤ በፍጹም፡፡ ጤፍ በሚናው ይልቃል፡፡ የጭብጥ ክትትል ከመፍጠር፣ የመተርጎሚያ ዐውድ ከመተለም ባለፍ ዝርው ህልውናም አለው፡፡ ጤፍ በቤት ውስጥ ቁስነት ተከስቷል፤ የግድግዳ ምርጊት ሆኖ ተገልጧል፤ ወዘተ፡፡ ጤፍ ታሪክ ነው፤ ምጣኔ ሀብት ነው፤ ፖለቲካ ነው፤ ርእዮተ ዓለም ነው፡፡ በጤፍ የሰው አካል ተገንብቷል፤ የሰው ገጽ ተነድፏል፡፡ ገጻተ ሰብኡ ከጤፍ መልኩንም ይዘቱንም ወርሰዋልና ወደ ጤፍነት ተለወጡ ማለትም እንችላለን፡፡ ከተጨባጭ ሁነቶችና ህልውናዎች ባለፈ ጤፍ ለልእለ አካላዊ ክስተቶች ማድሪያነት ውሎም እንመለከታለን፡፡ ለምሳሌ፣ “ጓዳና ግርግዳ” የሚል ርእስ በተሰጠው፣ በቀጫጭን ዘንጎችና በጥቁር ጤፍ ትግግዝ በተቀናበረ ግድግዳ ላይ (በጤፍ ቡኮ የተመረገ፣ ጋሻ ያዘለ ግድግዳ) ከያኒው ይሁነኝ ብሎ በተዋቸው ሽንትር ሽንቁሮች ውስጥ አሳልፈን የምናየው “የቤተ ክርስቲያን” ጨርቅ ልእለ ፍጥረት ህላዌ ከልደትና ሞት ጋራ የታተመበት ነው፡፡ በመሆኑም ጤፍ በትርኢቱ ውስጥ የነገረ ሰብእን ዕጣ የምናሰላበትን ስብርባሪ አፍታ ጭምር ይሰጠናል ማለት ነው፡፡
በትርኢቱ ውስጥ በጤፍ ከተገነቡ ምስሎች መካከል ገጸ ሰብእ[11] የተነደፈው በሁለት ተከታታይ ትዕይንቶች ውስጥ ብቻ ነው፤ በ“Gluten-free-dom I” እና በ“Gluten-free-dom II”፡፡ እነዚህ ትዕይንቶች “ተከታታይ” ብለን ብቻ የምናልፋቸው አይመስሉኝም፡፡ ይልቁንም እጅግ በተወሳሰበ ትእምርታዊነትና በተራቀቀ ዘይቤ የተከየኑ፣ ለፈርጀ ብዙ ንጽጽርና ትርጓሜ የተመቹ ወደረኛ ቅርጾች ናቸው፡፡ ኋለኛውን መነሻ እናድርግ፡፡ ጀርባ ለጀርባ እንጂ ፊት ለፊት የማይተያዩ፣ ትከሻ ለትከሻ ገጥመው ክብ የሰሩ የሰባት ነፍሰ ጡሮች ትዕይንት ነው፡፡ በዚህ ትዕይንት ውስጥ ሴቶቹ ክብነቱን ጠብቆ በጠባቡ በሚዞራቸው ቡላ ቀለም ያለው የአመድ ደለል ላይ ቆመዋል፡፡ ደለሉን ተከትሎ በክቡ የሰፈነው ነጭ አመድ ከሸማ የተሠራ ምንጣፍ፣ በዙሪያው የተኮለኮለው የከሰል ሰልፈኛ ደግሞ ጥቁር ጥለት ይመስላሉ፡፡ በሆዳቸው ፍሬ የያዙ ሰባት ሴቶች የተደራረቡ እጆቻቸውን ሐፍረታቸው ላይ ጣል እንዳደረጉ፣ እንጀራ የለበሰ ጋሻ አናታቸው ላይ እንደደፉ፣ በአክብሮት ይሁን በፍርሐት አልያም በሐፍረት አቀርቅረዋል፡፡
ሁለተኛው ትዕይንት የአንድ ሰው “ገድል” ነው፡፡ ይህንን ገድል እኔ “ገልና ገልቱ” ብዬ እጠራዋለሁ፡፡ (“ገል” የጋን ስባሪ፤ “ገልቱ” ያልሠለጠነ፣ በድንቁርና የተደፈነ፡፡) ዙሪያውን በተሰባበሩ ሸክላዎች የተከበበ፣ ከምድር ከፍ ብሎ የታነጸ፣ ባለ ስድስት ማዕዘን ቅርጽ ያለው ጡብ ገዝፎ ይታያል፡፡ ሙቀት ፍለጋ እጆቹን ወደ ፊት የዘረጋው ሰው እጡቡ አናት ላይ ባፍጢሙ እደፋው የአባቶቹ ጋሻ ላይ “ተመቻችቶ” ተቀምጦ “የደቀቁ የሸክላ ገሎችን በተመስጦ ይሞቃል”፡፡ ሁለቱ ትይዕንቶች የመከታተል ብቻ ሳይሆን እርስ በእርስ የመተረጓጎም ባሕርይም አላቸው፡፡ ይህንን ለማጤን እላይ በገለጻዎቹ ውስጥ የሰፈሩትን ወደረኛ ድርጊቶችና ሁነቶች ማነጻጸሩ ብቻ በቂ ይመስለኛል፡፡
ሴቶቹ በገዛ ፈቃዳቸው ፋታ ለማይሰጥ፣ ድካም ለበረታበት፣ ህመም ላለበት ኃላፊነት ራሳቸውን የሞሸሩ ይመስላሉ፡፡ አንድም የቁጥራቸው ሰባትነት የኃላፊነቱን ክብደት ያጸናል፡፡ ሰባት ቁጥር በትውፊት፣ በሃይማኖት፣ በኪነት፣ ወዘተ. ውስጥ ምልዐትን፣ ፍጹምነትን ለማመልከት ተመላልሶ የሚመጣ ነባር መባያ ነው፡፡ ፍጹምነቱና ሙሉነቱ የበረከትም የቅጣትም ሊሆን ቢችልም፡፡ አንድም ሴቶቹ የቆሙበት የአመድ ደለልም ሆነ አካላቸው ተገጣጥሞ የፈጠረው የቅርጽ ክብነት እላይ በቁጥር ጸና ያልነውን በድካምና በህመም የተሞላ ኃላፊነት ፍጹም ያደርገዋል፡፡ በክብነት ውስጥ መውጫ ቀዳዳ ይጠፋል፤ መነሻና መድረሻ ይታጣል፡፡ ለእረፍት የሚሆን ጥጋት አይሰጥም፡፡ በቀለ በምስሉ መግለጫ ላይ በገሀድ እንደሚጠቁመን ሰባቱ ሴቶች በዝርው ሰባቱን ቀናት ይወክላሉ፡፡ በዚህም ሰንበት ተገድፏል፤ የለመድነው የጊዜ መስፈሪያ ተሽሯል፡፡ ቀናቱ በሴቶቹ ድርጊት ተቃኝተው “ጊዜ” ከሰው ጋራ የሚለያይበት መስመር ደብዝዟል፡፡ መነሻ፣ ማጋመሻ፣ መዳረሻ የሚባሉ አንድም፣ የድርጊትና የሁነትና መሥፈሪያዎች፤ አንድም የጊዜ ዋቢዎች ሳስተዋል፡፡
እላይ በእንጥልጥል ወደተውነው ጉዳይ እንመለስ፤ “ገሎችን መሞቅ” ምን ማለት ነው? ከከያኒው ምስክርነት ባሻገር የወጣቱ የእጅ አዘረጋግ ሁኔታ በሙቀቱና በአካሉ መካከል በፈጠረው ሚዛን ሙቀትና ምቾት መኖራቸውን እንረዳለን፡፡ ግን እሳቱ ወዴት ነው? የሙቀቱ ምንጭስ ምንድ ነው? ለእነዚህ ጥያቄዎች በአንድምታ የምንገልጠው እውነታ ካልሆነ በቀር፤ በቀጥታ የምናገኘው መልስ ያለ አይመስለኝም፡፡ በባለ ስድስቱ ማዕዘን ጡብ ዙሪያ በሰፊው የፈሰሱት የገል ስብርባሪዎች በኢትዮጵያውን የቆየ ታሪክ ውስጥ ቋሚ ሥፍራ ያላቸው፣ በሸክላ የተሠሩ አገረ ሰብአዊ ዕደ ጥበባት ናቸው፤ በየዓይነቱ --የጀበና፣ የምጣድ፣ የድስት፣ የጋን፣ የጣባ፣ የዕጣን ማጨሻ፣ ወዘተ. ስብርባሪዎች፡፡ ስብርባሪዎቹን በቅርበት ላጤነ ሰው ዕደ ጥበባቱ በእርጅና ምክንያት ከሰርክ ግብራቸው የተገለሉ አይመስሉም፡፡ ይልቁንም ከነወዛቸው ከነጉልበታቸው ያሉ፣ ከግብራቸው በግድ ተነቅለው የደቀቁ ነው የሚመስሉት፡፡ በሌላ ቋንቋ ሙቀቱ የሚመነጨው ከገሎቹ ትኩስነት ነው፡፡ ትኩስነት፤ አንድም፣ ከእሳት ምድጃ የሰበሰቡትን ሙቀት ይዞ ማቆየት ነው፡፡ ገልቱው ዕደ ጥበባቱን ከተሰየሙበት ምድጃ ላይ ነቅሎ --ቡናና ወጡን ደፍቶ፣ ዳቦና እንጀራውን ገልብጦ--ጀበናውን፣ ድስቱን፣ ገበር ምጣዱን፣ ምጣዱን አንክቶ፣ እንካቹን ሜዳ ላይ ዘርቶ ትኩስነታቸውን እየሞቀ ነው፡፡ አንድም በዘይቤ ተራ እንናገርና ትኩስነት አፍላነት ነው፡፡ የአገልግሎት ዘመን አለመጋመስ፡፡ ከብርታትና ጥንካሬ ጋራ መሆን፡፡ ጠላውን ደፍቶ፣ እርጎውን ገልብጦ፣ ወዘተ. ያደቀቃቸው የሸክላ ውጤቶች፡፡
በዚሁ ተጠየቅ ከተጓዝን የሴቶቹን አቋቋም በመመርመር በሰባት ቁጥር እና በክብ ቅርጽ ትግግዝ ጸና ያልነውን ህመም በተጨባጭ መመልከት እንችላለን፡፡ የሴቶቹ ፋታ የለሽነት ድርጊቶቹንና ሁነቶቹን በሙሉ ወደማያቋርጥ ሂደትነት ለውጧቸዋል፡፡ ይህንን ለማጤን--በተለመደው አገላለጽ--እንጀራ የጠመጠመ ጋሻ ከሰፈነበት የራስ ጸጉራቸው፣ በአመድ ደለል እስከተደበቀው የእግር ጥፍራቸው ድረስ መመልከቱ በቂ ነው፡፡ አመዱ እና እንጀራው ትይዩ ናቸው፤ አንዱ ምርት ሌላው ግርድ፡፡ ከአናት እንጀራው በተመረተ ቁጥር ከስር አዲስ አመድ ይወድቃል፡፡ አዲስ አመድ --ትኩሣቱን ያልጨረሰ አመድ፤ ረመጥ፡፡ ይህ ማለት ሴቶቹ ረመጥ ላይ ቆመዋል እንደማለት ነው፡፡
ቀደም አድርጌ ለማሳየት እንደሞከርኩት ሴቶቹ እንዲህ ያለውን በድካምና በህመም የተሞላ ኃላፊነት በፈቃዳቸው መርጠው ተቀብለዋል፡፡ በማሕፀኗ ሽል የያዘችን እናት በረመጥ እስከመድበን የሚያደርስ መስዋዕትነት ምን የሚሉት ኃላፊነት፣ እንዴት ያለ ዓላማና ተልእኮ ነው? የራስን ሰብእና የሚያደቅቅ፣ ህልውናን የሚያመነምን፣ ሕይወትን የሚያሰልል ተግባር ውስጥ በፈቃድ መሳተፍ ራስን ለከፋ ጉዳት ማጨት ይመስላል፡፡ የፈቃድ ጉዳት (self-destruction)፣ ከፍ ሲልም የፈቃድ ሞት ከዳግም ልደት ጋር የሚዛመዱበት እንዲህ ያለው አቀራረብ ሚታዊ አመሳሰል ነው፡፡ ይህን ዓይነቱን አመሳሰል በሚቶሎጂ ውስጥ በብሉየ መዋዕልና[12] ደንብ ከተቀረጹ ምስሎች (archetypal imageries) ጋራ አቆራኝተን መመልከት እንችላለን፡፡ በሆዳቸው ፍሬ የያዙ ሴቶች ትከሻ ለትከሻ ገጥመው ክብ መሥራታቸው፣ በሠሩት ክበብ ውስጥ ረመጥ ላይ መቆማቸው፣ በአመድ ደለል መያዛቸው፣ እንጀራ “ማብቀላቸው” በአንድ ግዜ ኦሮቡረስን (በክብነት) እና ፊኒክስን (በረመጥነት-አመድነት) አቃልጠን እንድናስብ ያደርገናል፡፡ ራሷን አቃጥላ ከትቢያዋ ላይ ነፍስ የምትዘራው ፊኒክስ (Phoenix) እና በክብ ቅርጽ ከጅራቱ አንስቶ ሙሉ አካሉን በልቶ በአዲስ ህልውና የሚከሰተው አሮቡሮስ (Ouroborus) “ሁለንተናዊ” ሊባሉ የሚችሉ የህመምና ድኅነት፣ የሞትና ልደት ትእምርቶች ናቸው፡፡ ባዶ እግራቸውን ረመጥ ላይ የቆሙ ሰባት እናቶች በቸልታ የተጎዳውን ነባር ምንትነት፤ በሆዷቸው የያዟቸው ሰባት ፍሬዎች ደግሞ እንደ አዲስ ይወለድ ዘንድ የሚጠበቀውን ርእይና ርእዮት ይወክላሉ፡፡ ከዚህ ትዕይንት ዓላማዎች መካከል አንዱና ምናልባትም ቀዳሚው ለዘመናት ለኖረው፣ ዳሩ ግን ቸል ለተባለው የእናቶች ህመምና ድካም--የላቀ ብሔራዊ ተግባር--ዕውቅና መስጠት ነው፡፡ ይህ ዕውቅና ልዕለ ሰብአዊ እና ልዕለ ታሪካዊ እንጂ ተርታና ሰርካዊ አይደለም፡፡ በሌላ ቋንቋ፣ ከያኒው ከፍ ባለ የአከያየን ስልትና ርእዮት እናቶችን ጥልቅ ጊዜ ውስጥ በመትከል ወደ ሚታዊ ተጋዳሊነት ቀይሯቸዋል፡፡ በምላሹም ከዚያው ጥልቀት ውስጥ በጽናት የሚቆም ብሔራዊ ትእምርት እና ብሔራዊ ምንትነት ለማስገር ሞክሯል፡፡
አንድም እናቶች ካለመኖር ህጽን መኖርን አስገኝተዋልና ለዚያም ኪናዊ ውዳሴ እንደ ማውረድ ሊቆጠር ይችላል፡፡ በአንዳንዶች ግምት “ጤፍ” የሚለው መጠሪያ “ጠፋ” ከሚለው ቃል የተገኘ ነው፤ ጠፋ፣ መኖር አቆመ፣ ህልውናው አበቃ እንደማለት፡፡ በሌላ ቋንቋ የዚህ የእህል ዘር የመጠን አነስተኛነት ከመኖር ይልቅ ላለመኖር ይቀርባል እንደማለትም ነው፡፡ የ“ጤፍ” የፍቺ ነቅኡ “ጠፋ” የሚለው ግስ ከሆነ፣ አንድም፣ ጤፍ የምንለው፣ በጣት የምንቆነጥረው ደቃቅ ነገር በተጨባጭ አለመኖርን ያስተማስላል (the representation of absence, the visibility of invisibilty) እንደማለት ነው፡፡ አንድም ዐውራውን የብሔራዊ ሚቶች መሻት--የመነሻዎች ሁሉ መነሻ የመሆንን፣ ከምንምነት ነቅእ የመፍለቅን መሻት--ይጠልፍልናል፡፡ ጤፍ አለመኖርን ከወከለ ከጤፍ የምንጠልቀው “ኢትዮጵያዊነት” ከእመ አበ አልቦ እንደተገኘ (creation ex nihilo, that is, creation from nothing) ይቆጠራል፡፡ በዘይቤ ተራ እንነጋገርና የኢትዮጵያ ገበሬ “አለመኖርን” ይዘራል፡፡ እናቶች ደግሞ ከአለመኖር ማሕጸን “እንጀራን” የመሰለ ግዙፍ ኑባሬ ያዋልዳሉ እንደማለት ነው፡፡ ከጤፍ አብራክ እንጀራ የመክፈሉን ጉዳይ፣ እናቶቹ በሆዳቸው ከያዙት ጽንስ መወለድ ጋራ አቆራኝቶ ማየት ይቻላል፤ ያ ጽንስ አንድም በነባርና በአዳዲስ እሴቶች ትብብር ይሸመናል ያልነው “ኢትዮጵያዊነት” (pan-Ethiopianism) ነው፡፡ የእንጀራው አናት ወጥቶ በጋሻ ቅርጽ መስፈኑ ደግሞ የልደቱ መፈጸም ማረጋገጫ ትእምርት ነው፡፡ ጋሻ የአርበኝነትና የነጻነት ትእምርት፤ ጤፍ ደግሞ የኢትዮጵያና የኢትዮጵያዊነት ማደርያ ነው ካልን፣ በጋሻ መልክ የተከሰተው እንጀራ የዚህ ማረጋገጫ ሰንደቁ (the symbol of national imaginary) ይሆናል፡፡ አንድም በጋሻ ቅርጽ አናታቸውን የከበበው እንጀራ በሰማዕትነት እንዳገኙት የብርሃን አክሊል (halo or nimbus) ሊቆጠር ይችላል፡፡ እንዲህ ያለው ሐቲት ለኪነቱ በ“በብሉየ መዋዕልና” ደንብ ኢትዮጵያንና ኢትዮጵያዊነትን አጥልቆ የሚተክልበትን ረቂቅ ዐውድ ይሰጠዋል፡፡
ኢትዮጵያውያን አንጀራን መመገብ የጀመሩበትን ጊዜ የሚያመለክት እርግጠኛ መረጃ የለም፡፡ ነገር ግን የእንጀራን መነሻ የሚጠቁሙ፣ ዘመኑን እስከ ቅድመ ክርስቶስ እስከ 100 ዓ.ዓ.
የሚያደርሱ የቃል ተረኮች እንዳሉ ስትዋርትና አስናቀ ይናገራሉ (1962: 127)[13]፡፡ በእነዚህ ተረኮች ወስጥ እንጀራ ኢትዮጵያውያን በተቸገሩ ወቅት ከልእለ ፍጥረት ህላዌ የተሰጠ በረከት ተደርጎ ነው የሚቀርበው፡፡ (በበቀለ ኪነት ውስጥ ያንን ሚና ወደ ሚታዊ ህልውናነት የተሸጋገሩት እናቶች ወስደውታል):: ቀደም አድርገን የጠቀስነው የታደሠ ጥናት እንደሚያመላክተን (2017፣ 50) ከኢትዮጵያ ሕዝብ ውስጥ 70 ከመቶ ያህሉ ጤፍን በእንጀራ መልክ ተመጋቢ ነው፡፡ ይህ ቁጥር የጤፍ እንጀራን ለብሔራዊ ምግብነት የሚያበቃው ይመስለኛል፡፡
ጋኖቹን[14] አንክቶ፣ ባፍጢሙ እደፋው ጋሻ ላይ ተቀምጦ ስብርባሪ ገሎች እየሞቀ በምቾት የሚመሰጠው ገልቱ በፈንታው ፍቺው የዚህ ተቃራኒ ነው የሚመስለው፡፡ በእኔ አረዳድ ትዕይንቱ የዘመናችን ክፉ አባዜ--አገር ለዘመናት ጸንታ የኖረችባቸውን የዕሤት ሥርዓቶች፣ የጋራ ታሪኮች፣ የወል ልቡናዎች የመቀናቀን አባዜ--በስላቅ የተነደፈበት ነው፡፡ ስላቁ የቤቱን ማገር እየመዘዘ በሚያነድድ፣ መሠረቱን እየቆረቆረ ቤቱን ራሱ ላይ በሚንድ ገልቱ ላይ ቢያርፍም፣ አገራዊ አደጋው የምር እና ቅርብ መሆኑን ትላልቅ ጋኖችን በማውደም አሳይቷል፡፡ አገር ጸናባቸው ያልናቸው ረቂቅ ዕሤቶች ወጣቱን በከበቡት ስብርባሪ ገሎች ገዝፈው ይታያሉ፡፡ “ጋን” ከአገረ ሰብእ ጥበብነቱ ባሻገር አገር አጽንተው ያቆዩትን ረቂቅ ዕሤቶች ለመወከል የሚያበቃ ሥነ ልሳናዊ እና ሥነ ፍቻዊ ባሕርይ አለው፡፡ በተለይም ቃሉ “ጋኖች” ተብሎ በብዙ ቁጥር ሲጠራ የፍቺው ስፋት ከማጀት እስከ አደባባይ ይዘልቃል፤ “ጋኖች፤ ትልልቆች ሰዎች ዋኖች ጨዎች ጎምቱዎች አባቶች ዐዛውንቶች፡፡ (ተረት)፤ ጋኖች ዐለቁና ምንቸቶች ጋን ኾኑ” (ደስታ ተክለ ወልድ፣ 280)፡፡ አንድም፣ ከማጀት እስከ ቤተ መንግሥት የተዘረጋ ፍቺ አለው፤ ከጠላ መጥመቂያ፣ ከጠጅ መጣያ ቁስነት እስከ ንጉሥ መጠሪያት የሚደርስ ፍቺ፤ የጃን ሆይ አቻ ሆኖ፣ “ጋን ሆይ ፤-ገናና ሆይ፤--ጃን ሆይ፡፡” (280) እያስባለ፡፡
እስካሁን ለማሳየት እንደሞከርኩት Gluten-free-dom “I” እና “II” በተወሳሰቡ ትእምርቶች እና በተራቀቁ እይታዊ ሜታፈሮች የተከየኑ ድንቅ ምስሎች ናቸው፡፡ በምስሎቹ መካከል የሚካሄደው ንጽጽር ከዚህም አልፎ ልሄድ ይችላል፡፡ እኛ ይህን በይደር ዘግተን ለመጣጥፉ እንደ ማሳረጊያ ወደሚያገለግሉ አንድ ሁለት ነጥቦች እንለፍ፡፡
IV
በትርኢቱ ውስጥ ከቀረቡት ሥራዎች ብዙዎቹ --ከፀሐይ እና ጎጆ (ከባህል እና ተፈጥሮ ) መስተጋብር ከተቀሰቀሱ የሰርክ ደፋ ቀናዎች (“አሁንና ቅድም” I፣ II፣ III)፣ የዘወትር ስሜቶች (“አዙረኝ አዛዙረኝ”) አንስቶ፤ ረቂቆቹ የወል ዕሤቶች፣ የጋራ ልቡናዎች እስከተከተቡባቸው ምስሎች (“ጓዳና ግድግዳ”፣ Gluten-free-dom “I” እና “II”) ድረስ ከጤፍ እና ከጋሻ ትእምርታዊ ተራክቦ የተገኙ ናቸው፡፡ እርግጥ ነው እንዲህ ካለው የትርኢት ጠቅላይ ፈለግ የሚሸሹ ጥቂት ሥራዎች አይጠፉም፡፡ ለዚህ ደግሞ፣ “የገደል ማሚቶ”፣ “ቆሜ ተቀምጬ” እና “አዲስ ጠላ በሰባራ አንኮላ” አብነት ይሆናሉ፡፡ “የገደል ማሚቶ” ለኀልዮ እምብዛም ያልተጨነቀ፣ ምናልባትም የሄደ ድምጽ ተመልሶ የሚመጣበት የቅርጾች ጨዋታ ነው፡፡ በ“አዲስ ጠላ በሰባራ አንኮላ” ውስጥ የጤፍና የጋሻን የተናጠልም ይሁን የወል ህልውና በገሀድ ፈልገን ስለማናገኝ ሥራው ከትርኢቱ አጠቃላይ መንፈስ ያፈነገጠ ይመስላል፡፡ ይሔ ግምት ግን ኪነቱን ከቀሪዎቹ ሥራዎች ጋራ አናብበን መተርጎም ስንጀምር በቀላሉ የሚፈርስ ነው፡፡ እንዲህ፣ እንደ “ጤፍና ነጻነት” ባለ አንድ ወጥ ርእስ በተሰጠው ከፍ ያለ ትርኢት ውስጥ ሥፍራ ያገኙ፣ በተቀራራቢ የጊዜ ክበብ ውስጥ የተከየኑ ሥራዎች በአመዛኙ ተነጥሎ ከሚከናወን ዝግ ምልከታ ይልቅ ለአጎራባች (co-textual) እና ለዐውዳዊ (contextual) ምርምር ይጋብዛሉ፡፡ ይህንን አጠቃላይ የነገረ ፍካሬ መርህ ከግምት ካስገባን፣ ከያኒው በምስሉ መግለጫ ላይ ባቀረበው ፍቺ ብቻ ረግተን የምንቆም አይመስለኝም፡፡ ይልቁንም በአንድምታ ተጨማሪ ትርጉም ለማከል እንጋበዛለን፡፡ በእኔ እምነት በትርኢቱ ውስጥ በአካል ጭምር የተጎራበቱት Gluten-free-dom “I” እና “አዲስ ጠላ በሰባራ አንኮላ” ከጤፍ እና ጋሻ መጉደል ባሻገር በገሎቻቸው ተሳስበው በመንፈስ ይሰምራሉ፤ በጭብጥ ይከታተላሉ፡፡ በትርጓሜም እንደሚከተለው ይተጋገዛሉ፡፡
በጥንታዊው የሒሳብ ማሰላሰያ፣ በአባከስ አምሳያ የተበጀው በአራት ማዕዘን የብረት ፍሬም የታጠረ ምስል፣ ብረቱ ላይ ሻጥ ሻጥ ተደርገው አግድም የተዘረጉ ወልጋዳ የእንጨት ዘንጎች፣ በዘንጎቹ ላይ የሚንሸራሸሩ በቅርጽ
ሠዓሊና ቀራፂ ፕሮፌሰር በቀለ መኮንን
(ሂላሪያ ተስፋዬ እና ዕዝራ እጅጉ ተወዳጅ ሚድያ)
#ፕሮፌሰር በቀለመኮንን ለተወዳጅ ሚድያ የቅርብ ወዳጅና ቤተሰብ ነው። የምንሠራውን የስነዳ ፕሮጀክት በሙሉ ልብና መንፈስ የሚደግፍ ቀና ምሁር ነው። ታናሾቹን ለማገዝ በቀዳሚነት የሚሰለፍ ኩራት ያልፈጠረበት ታላቅ ወንድም እንደማለት ነው። ከ4 ዓመት አስቀድም "መዝገበ አእምሮ" ቅጽ አንድ ሲዘጋጅ ከጀርባ እና ከጎን ሆኖ ሲረዳን ነበር። የኃይሉ ልመንህን ታሪክ ፕሮፌሰር በቀለ አስታውሶ ታሪኩን ባይነግረን ኖሮ ኃይሉ ልመንህን አናገኘውም። ፕሮፌሰር በቀለ ሌሎችም ስሙን ከአክብሮት ጋር የሚያነሱት የሥነጥበብ ሰው ነው።
#ተወዳጅ ሚድያ እስከዛሬ የ432 ባለሙያዎችን ታሪክ በመፅሐፍ፣ በዲጂታል ሚድያ እና በድምፅ ሲሰንድ ፕሮፌሰር በቀለ መኮንንም እንዲካተት አድርጓል። እስከዛሬ በሚዲያ እና ኪነ-ጥበብ ዘርፍ የሠሩትን በምንችለው አቅም ታሪካቸው ዘመን እንዲሻገር ያደረግን ሲሆን የስነዳ ተግባሩም ተጠናክሮ ቀጥሏል። በቀጣይ እያዘጋጀነው ባለነው ዕትም ከ20 ዘርፎች የተውጣጡ ታላላቆችን በማሰባሰብ ላይ እንገኛለን ። ከእነዚህ ታላላቆች ውስጥ ፕሮፌሰር በቀለ መኮንን አንዱ ነው። የሕይወት ታሪኩንም ብዙ ካልታዩ የልጅነት ምስሎቹ ጋር አንድ ላይ በማድረግ ታሪኩን አጋርቶናል። ዕዝራ እጅጉ እና ሂላሪያ ተስፋዬም ታሪኩን እንደሚከተለው ሰንደውታል።በነገራችን ላይ በዚህ የሕይወት ታሪክ መጣጥፍ ውስጥ ተባባሪ ፕሮፌሰር ቴዎድርስ ገብሬ "በቀለን በብሔራዊ ትእምርት ፍለጋ ውስጥ" ብሎ የጻፈው ረዘም ያለ ምሁራዊ ትንተና አቅርበናል። የፕሮፌሰር በቀለ መምህር ወርቁ ጎሹ የሰጡትንም ምስክርነት አካተናል። መልካም ንባብ።
#የሰባተኛ ክፍል ተማሪ እያለ የስዕል ዝንባሌውን እንዲከተል እንዲሁም የስዕል ትምህርትን እንዲማር ያመለከቱትን መምህሩን በአንደበቱ ቃላት ይስላቸዋል። እኚህ መምህሩን፥ “ሊከተሉት የሚገባ ሰው” ሲል ይገልጻቸዋል። ምንአልባት ከበርካታ ዓመታት በኋላ እርሱ ራሱም እንዲያ ያለ ‘ሊከተሉት የሚገባ’ የጥበብ ሰው ሊሆን እንደሚችል አልገመተ ይሆናል።
#ፍላጎቱ ከእኩዮቹ የተለየ፣ ‘ተርታ’ ለሆነ ነገር መሻት የሌለው፣ በለጋ እድሜው ሳይቀር ነገሮችን እንደሆኑ ማየትና መሥራትን የማይመርጥ፣ አዲስ ነገር መፍጠርን አልያም የነበረውን በአዲስ መልክ መቃኘት ይቀናው የነበረ ተማሪ ነው። ስሙን ሳይቀር በስዕል ይጽፍ እንደነበር ይናገራል። በስጋው ላይ ያሠለጠናት ነፍሱ፥ ሰዓሊ የመሆን ግቡን ለማሳካት ይችል ዘንድ ‘የሰው ልጅ መሠረታዊ ነገሮችን’ አሻግሮ እንዲያይ ጉልበት ሰጥታዋለች። ይህ ጉልበትና ጽናት ነው፣ አሁን በሥነ ጥበብ ዘርፍ በኢትዮጵያ የመጀመሪያውን ሙሉ ፕሮፌሰር የወለደው፥ ሠዓሊና ቀራፂ ፕሮፌሰር በቀለ መኮንን።
#ትውልድና እድገቱ ደብረዘይት (ቢሾፍቱ) ከተማ ነው። ጥር 6 1956 ዓ.ም። ትምህርትን አሃዱ ያለው በቆሎ ትምህርት አቡጊዳ ብሎ ፊደል ቆጥሮ፣ ዳዊት ደግሞ ነው። የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርቱን አፄ ልብነ-ድንግል ወናግሰገድ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት፣ እንዲሁም ኹለተኛ ደረጃ ትምህርቱን በዚያው ደብረዘይት ልዕልት ተናኘወርቅ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተከታትሏል። የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ ፈተናውን የወሰደው ደግሞ በአዲስ አበባ ምኒልክ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ነው።
ከልጅነት እድሜው ጀምሮ የተገዛው ለስዕል ጥበብ ብቻ ሳይሆን በጠቅላላ ለጥበብ ነበር። አዲስ ነገርን አልያም የነበረው በተሻለ መንገድ ሆኖ ማየትን ይመርጣል። በጥበብ ለሚሠራ ነገር ሁሉ ልዩ ፍቅር አለው። አሁን በአዋቂነትና በርቱዕ አንደበቱ ውበት እንደሚገዛው፥ ሰው የማይሠራውን መሥራት አልያም የተሠራውን ነገር ባልተሠራበት መንገድ መሥራት እንደሚወድድ ይናገራል። ይህን ቃሉን በልጅነት እድሜው ሲገልጥ ደግሞ፣ ስሙን ሳይቀር በስዕል ይጽፍ ነበር።
#የተካነበት፣ የሠለጠነበትና የታወቀበት የስዕል እና የቅርጻ ቅርጽ ጥበብ ይሁን እንጂ፥ ለጽሑፍ ጥበብ እና ውበትም ስሱ ነው። በልጅነትና ወጣትነት እድሜው በደብረዘይት ኪነት ውስጥ ቴአትር፣ ግጥም እንዲሁም መፈክር ጭምር በመጻፍ ይታወቃል። እንደውም ለተማሪዎች፣ ለሰፈሩ ወጣቶች የጻፋቸው የፍቅር ብሎም ልዩ ልዩ ደብዳቤዎችና ግጥሞች ጋር በተያያዘ በተለያየ አጋጣሚ የሚያነሳቸው ገጠመኞቹ ጥቂት አይደሉም። የእጅ ጽሑፉን ብቻ ሳይሆን የሚጽፋቸው ጽሑፎችና ግጥሞች ይዘት ጭምር ነበር ብዙዎችን የሚስበው።
#በኋላ 12ኛ ክፍል ፈተናን ከመውሰዱ አስቀድሞ፥ የስዕል ትምህርትን ለመማርና መምህሩ የዘራበትን ዘር ለማፍራት ዝንባሌውን ተከትሎ በዘመኑ አዲስ አበባ የሥነ ጥበብ ትምህርት ቤት (አሁን አለ ሥነ ጥበብና ዲዛይን ትምህርት ቤት) አቀና። ትምህርት ቤቱን ለመቀላቀል ደጅ ጥናትና ምልልስ እንዲሁም ተማጽኖ አስፈልጎታል። በኋላም ተሳክቶለት ተማሪ ለመሆን በሚጠበቀው ፈተና አንድ ሺህ ከሚጠጉ ተወዳዳሪዎች መካከል ከ14 አላፊ ተማሪዎች አንዱ መሆን ቻለ።በ1971።
#በአንድ ወቅት በአራዳ ኤፍኤም አዲስ አራዳ የራድዮ ፕሮግራም ላይ ባደረገው ቆይታ፣ የዚያን የአምስት ዓመት የትምህርት ዘመን ሲያነሳ፥ በትምህርት ቤቱ የነበረው የ5 ዓመት ቆይታ ቀላል እንዳልነበር ያስታውሳል። ሌሊት ማረፊያ የሚያጣባቸው ቀናት ብዙ ናቸው። ምንም እንኳ ለአምስት ዓመታት እያንዳንዱ ቀን የአንድ ዓመት ያህል ከባድ የነበር ቢሆንም፥ እርሱ ግን ‘ቀኑን ጎበዝ መሆን ነበር የሚፈልገው’። እናም ቀኑን ጎብዞ ከባዱን ጊዜ በብልሃትና በጽናት ተወጣው። ትምህርቱን አጠናቅቆም በማዕረግ ተመረቀና እዚያው የተማረበት ትምህርት ቤት መምህር ሆኖ ተቀጠረ።
በተማረበት ትምህርት ቤት በወጣት መምህርነት ለአራት ዓመታት አገልግሏል። ከዚያ በኋላ፥ ወደ ሩሲያ ለከፍተኛ ትምህርት ተላከና ሞስኮ ከተመ። ‘ግራጫ’ ይለዋል፣ የሩስያን ፀሐይ አልባ ቀዝቃዛና ደመናማ የጨላለመ የዘመኑን ድባብ። በዙሪያው ውበትን ማሰስ የለመደ ዐይኑ በሞስኮ ያንን ሊያገኝ አልቻለም። እንዲያም ሆኖ የደከመለት ትምህርቱን ለመፈጸም ጽናትን በመምረጥ፥ ከስድስት ዓመት የሞስኮ ቆይታ በኋላ የከፍተኛ የሥነጥበብ ትምህርቱን በሚገባ አጠናቅቆ ወደ እናት ሀገሩ ኢትዮጵያ ተመለሰ።
ከሩስያ መልስ አስቀድሞ በመምህርነት ያገለግልበት በነበረው ሥነ -ጥበብ ትምህርት ቤት የማስተማር እድል አገኘ። በዚያም በመጀመሪያ በሥነ ጥበብ ታሪክ ከዚያም በንድፍ ጥናት መምህር ሆኖ ቆይቷል። በመምህርነት ብቻም አይደለ፥ በጊዜው ‘አርት ስኩል’ ይባል የነበረውን ይህን ትምህርት ቤት፣ ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋምነት ለማሳደግ ከ1990ዎቹ ጀምሮ ለዓመታት በዘለቀውና በተደረገው እልህ አስጨራሽ ትግል ውስጥ ከፊት ሆነው ሲያስተባብሩ ከነበሩት መካከል ሆኗል። በመጨረሻም ከምክትል ጠቅላይ ሚኒስቴር ቢሮ በተሰጠ የጥናት ውሳኔ ሥነ ጥበብ ትምህርት ቤቱ ወደ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተዛውሮ የከፍተኛ ትምህርት ተቋም ሲሆን ትልቁን ድርሻ ከተወጡት ጥቂት ግለሰቦች መካከል ፕሮፌሰር በቀለ መኮንን ተጠቃሽ ነው።
ትምህርት ቤቱ የዩኒቨርሲቲው አንድ አካል ክፍል ከሆነ በኋላ የመጀመሪያው ዳይሬክተር በመሆን ሠርቷል። በዚያም ወቅት የትምህርት ቤቱን ነባር ስርዓት የከፍተኛ ትምህርት ስርአት ቅርፅ ለማስያዝ በብርቱ ለፍቷል፣ አሳክቷልም። በ2009 ዓ.ም ገደማ የሥነጥበባት ኮሌጅ ሲመሠረት በድጋሚ የትምህርት ቤቱ ዳይሬክተር ሆኖ ከማገልገሉ ባሻገር፥ ትምህርት ቤቱ መጠሪያው ወደ አለ የሥነ ጥበብና ዲዛይን ትምህርት ቤት የተቀየረው የኮሌጁ ዲን ሆኖ ባገለገለበት ዘመን ነበር። ከዚያም ባሻገር አዲስና ተጨማሪ የፊልም ትምህርት ክፍል እንዲቋቋም ከፍተኛ ጥረት በማድረግ ትምህርት ክፍሉ እውን እንዲሆን አስችሏል። ከዚህም ባሻገር በማስተማርና በማማከር በርካታ ተማሪዎችን ያፈራ ብርቱ ባለሙያ ነው።
#ፕሮፌሰር በቀለ በብሉይ ወይም ክላሲክ አካዳሚ ትምህርቱን ጠንቅቆ የተማረ ይሁን እንጂ በዘመነኛ የሥነ ጥበብ እንቅስቃሴ በኢትዮጵያና በአፍሪካ ከሚጠቀሱ ባለሙያዎች አንዱ ነው። አዳዲስ ሙከራዎችና አሰሳዎችን በድፍረት ግን በኃላፊነት በማከናወን ሁሌም ፈር ቀዳጅና አዲስ መንገድ የሚያሳይ ከልቡ የፈጠራ ሰው ስለመሆኑም ብዙዎች ይመሰክራሉ፥ ከዚያም በላይ ሥራዎቹ ምስክሮቹ ናቸው።
#ፕሮፌሰር በቀለ የመጀመሪያ የሥዕል ኤግዚቢሽኑን ያቀረበው ከሀገር ውጭ ፊንላንድ፥ ‘ኮ’ፕዮ’ የሚባል ዩኒቨርሲቲ (Kuopio - በአሁኑ ምሥራቅ ፊንላንድ ዩኒቨርሲቲ) ነበር። ይህም በሞስኮ የሥነጥበባት የመጨረሻ ዓመት ተማሪ እያለ ሲሆን፣ ለዕይታ ያቀረባቸው ሥራዎቹም የተለያዩ አስቀድሞ በትምህርት ቤት ቆይታው ያዘጋጃቸው ናቸው።
ከዚያ በኋላ ለቁጥር በርካታ፣ ለዓይነት ብዙ፣ ለዐይን ውብና አስደማሚ የሆኑ ሥራዎችን ያለማቋረጠ ለበርካታ ዓመታት ሲያቀርብ ቆይቷል። ከስዕል ኤግዚቢሽን እስከ አደባባይ ሐውልቶችና ዓለም አቀፍ መድረኮች፥ በቀለ መኮንን የሚለው ስም እንግዳ ሆኖ አያውቅም።
#በ1996 ዓ.ም ያቀረበው ‘እንቆቅልሽ’ የተሰኘ የ‘ኢንስታሌሽን ጥበብ’ ትርዒቱ ዘይቤያዊ (Methaphorical) ትርጉም የያዘና አሁንም ድረስ አነጋጋሪ ሆኖ የቆየ ሥራ አንዱ ተጠቃሽ ነው። በ2000 ዓ.ም ‘እድልና ምርጫ’ የሚል ‘ክሪቲካል’ ትርዒቱን አቅርቦ ተመልካቹን አስደምሟል። በ2010 ዓ.ም ‘ባሩድና ብርጉድ’ ሲል የሰየመው አነጋጋሪና አወያይ ኤግዚቢሽኑ፥ ተመልካቹ ስለ ሥነጥበብ ያለውን አመለካከት ደጋግሞ እንዲፈትሽ ያስገደደ ነበር።
በ2016 ዓ.ም በኢትዮጵያውያን የሕይወት ዘይቤ ላይ ትልቅ ጥያቄ አንስቶ ያወያየውንና እስከ አሁንም የሚያወያየውን “ግሉተን ፍሪ-ደም” ወይም ‘ጤፍና ነፃነት’ የተሰኘውን ልዩ ትርዒት አቅርቦ የሥነ ጥበብ ተመልካቾችን ማስደነቁና ማነጋገሩን ቀጠለበት።
ከ25 ዓመታት በላይ እነዚህን የፈጠራ ሥራዎቹን በሀገር ውስጥ እና በውጭ ሀገር በተለያዩ መድረኮች ሲያሳይ ቆይቷል። በአፍሪካ፣ በአውሮፓ እና በአሜሪካ፣ በተለያዩ ሙዚየሞች ሥራዎቹን አቅርቧል፣ ሐሳብና ዕይታውን አስደምጧል። ሀገሩን አልፎም አኅጉሩን አፍሪካን በዓለም መድረክ በዘርፉ በኩራት እንዲቆሙም ምክንያት ሆኗል።
#በቅርብ ማለትም ባለፈው 2017 ዓ.ም፥ በኢጣሊያ ቱሪን ከተማ ሮያል ፓላስ ሙዚየም ተጋብዞ ‘ዘ ስሞኪንግ ቴብል’ ወይም ‘የሚጤሰው ጠረጴዛ’ የተሰኘ ፀረ ቅኝ ግዛት ይዘት ያለው ዘመነኛ የሥነ ጥበብ ሥራ በመፍጠር ለዕይታ አቅርቧል። ይህም ከፍተኛ እድናቆትን ያስገኘለት ብሎም ሐሳቡን ያስደመጠበት አውድ መሆን ችሏል።
#መሥራት እንጂ ይህን ሠራሁ ብሎ መናገርን የማያዘወትረው ፕሮፌሰር በቀለ፣ እንዲህ ካሉ አውደ ርዕዮች ባሻገር በቀራጺነቱ የተጠበበባቸው ሥራዎችም እጅግ በርካታ ናቸው። ከቅርብ ዓመታት ወዲህ የሠራቸውን በማማከር የተሳተፈባቸውን ብቻ ለመጥቀስ፥ በሙሉ ነሃስ የተሠራው የቀዳማይ ኃይለሥላሴ ኪነ ሀውልትን ጨምሮ፥ አብርኆት የሕዝብ ቤተመጻሕፍት ደጃፍ የሚገኘው ኪነ ሀውልት (ከነሐስ ቀልጦ የተሠራው ሕፃን)፣ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ዋና መሥሪያ ቤት ያሠራው ሕንጻ ጋር የሚገኘው የባንኩን ዓላማና ርዕይ የሚያሳየው ግዙፍ ኪነ ሀውልት (ሀብት ካለ በሰማይ መንገድ አለ) እጅግ ጥቂቶቹ ናቸው።
ታድያ ለእነዚህና ለበርካታ ሥራዎቹ ሽልማቶችና እውቅናዎች ተበርክተዉለታል። ከእነዚያም መካከል በ1990 ዓ.ም የቺካጎ አርቲስቶች ዓለም አቀፍ ሽልማትን ያሸነፈ ብቸኛው አፍሪካዊ የስነ ጥበብ ባለሙያ መሆን ችሏል። እ.ኤ.አ. በ2006 በአሜሪካ ኒው-ዮርክ ውስጥ የIIE ፕሮግራም የሆነውን የ’Scholar Rescue Fund’ ሲቀበል የመጀመሪያው የሥነ ጥበብ ሰው ነበር። በዚያው ዓመት በባልቲሞር ሜሪላንድ ውስጥ በተጋባዥ ሠዓሊነት በበሜሪላንድ የአርት ኮሌጅ (MICA-Maryland institute college of Art) ለስምንት ወራት ቆይታ አድርጓል።
#ፕሮፌሰር በቀለ የኢትዮጵያ ሚሌኒየም ዓርማ ነዳፊ ሲሆን በመላ ሀገሪቱ በርካታ ኪነ ሀውልቶችን ነድፏል፣ አቅዷል፣ አማክሯል፣ መርቷል፣ ሠርቷል። በርካታ የመጻሕፍት ሽፋኖችንና የውስጥ ምስሎችን አዘጋጅቷል። በሀገር እና በዓለም አቀፍ የሥነጥበብ እና የሥነ ሕንፃ የውድድር መድረኮች ላይ በከፍተኛ ዳኝነት አገልግሏል። ከስነጥበቡ ማኅበረሰብ ውስጥ ደግሞ በኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ መደበኛ አባል ነው።
#ከዚህም በላይ ከእለት እለት የማስተማር ተግባሩ ጎን ለጎን በቅርቡ በተባበሩት መንግሥታት ፕሮጀክት ስር ነባሩ የአፍሪካ አዳራሽና የሥነ ጥበብ ሥራዎቹ እድሳት ውስጥ ባለሞያ፣ አማካሪና ተቆጣጣሪ በመሆን የተሳካ ሙያዊ ተልዕኮ ፈፅሟል። በአሁኑ ወቅትም በአለ ሥነጥበብ እና ዲዛይን ትምህርት ቤት የቅድመ እና ድኅረ ምረቃ ፕሮግራም ፕሮፌሰር ሲሆን፣ የዘመናዊ ሥነጥበብ ሙዚየም ገብረ ክርስቶስ ማዕከልንም በመምራት ላይ ይገኛል።
#ኅዳር 4 ቀን 2018 ዓ.ም የአለ የሥነጥበብና ዲዛይን ትምህርት ቤት የቀድሞ ተማሪዎች በትምህርት ቤቱ የአክብሮትና የምስጋና ፕሮግራም አድርገዉለታል። ተማሪዎቹ ያንን ያደረጉት ፕሮፌሰር በቀለ በጀርመን ሀገር ፍራንክፈርት ከተማ ከሚገኝው የሥነጥበብ ዩንቨርሲቲ ጋር ከዓመታት በፊት የተጀመረውን የኹለትዮሽ ግንኙነት ዳር በማድረስ ላደረገው ታላቅ ተግባር እና የትምህርት ቤቱን ዳግም ትንሳኤ ለማሳካት ድልድይ በመሆኑ በማመስገን ነው።
አሁን ታድያ ይህና ያልተነገረ እጅግ በርካታ፣ ውብና አስደናቂ፣ ገና ያልተተነተነና ዐይን የሚሻ ሥራን የሠራ ሰው ነው፥ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ አለ የሥነጥበብና ዲዛይን ትምህርት ቤት የመጀመርያው ሙሉ ፕሮፌሰር ማዕረግ የተሰጠው።
#ምንአሉ ?
ይህንን ዜና በደስታ በማኅበራዊ ገጾቻቸው ካጋሪት መካከል ጋዜጠኛ #ቴዎድሮስተክለአረጋይ እንዲህ አለ፥
“አንዳንድ ጊዜ ማዕረግም፣ ሹመትም፣ ሽልማትም በተለያዩ ምክንያትና አጋጣሚዎች ያልተገባ ሰው እጅ ውስጥ ሊገቡ ይችላሉ። ይህ ይበልጡን በሀገራችን፣ በዓለምም ላይ ታይቷል። ለፕሮፌሰር በቀለ መኮንን ዓይነቱ ደግሞ እንዲህ ግጥም ያለ ፣ በልኩ የተሰፋ ይሆናል። የበቄ ፕሮፌሰርነት በሥነ ጥበብ ዘርፍ የተሰጠ የመጀመሪያው ቢሆንም የሰውየው የበቀለ ብቻ አይደለም። የመጭው ትውልድ ሁሉ ነው። የሥነ ጥበብነት ብቻ ሳይሆን የመቻል ፕሮፌሰርነት ነው። ከእንግዲህ ለአንድ ጥበበኛ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሙሉ ፕሮፌሰርነት ማዕረግ መሰጠት እንደሚችል ማሳያው፣ ማመላከቻው፣ ዳገቱ፣ ምልክቱ ነው፥ በቀለ መኮንን። ያሉትና የመጭዎቹ የሥነጥበብ ልሂቃን ተስፋና ብርታት ነው። እንደሚቻል ማሳያውም፣ ማረጋገጫውም ሆኗል። ይህ ለሥነጥበቡ ብቻም ሳይሆን ለሙዚቃውም ፣ ለትያትሩም ነው።”
የሙያ አጋሩንናበአለ የሥነ ጥበብ እና ዲዛይን ትምህርት ቤት ዲን #ሠዓሊአገኘሁአዳነ በበኩሉ፥ “የቤት ሰው፣ መምህር፣ ባልደረባ፣ የሞያ አባት… ከፍ ሲል፣ ሲከብር፣ ድካሙ ፍሬ ሲያፈራ ወዘተ. ልብ ይሞላል። በቀለ መኮንን ንጉሡ ባለግዙፍ ሰብዕና፣ ከሰው ፊት የሚያቀረቡት፣ የሚያኮራ፣ ጥንቅቅ ያለ ሙያተኛ፣ በጥረቱ ከጉልበተኞች ቅሚያና ንጥቂያ፣ ከሰሜነኛው ንፍቀ ክበብ (global north) በር ጠባቂነት በጥበብ ሾልኮ በርካታ ዓለማቀፍ መድረኮችን የተጋራ፣ ረብ ያለው ተግባር እየፈጸመ ያለ ሰው የሚሠራበት ተቋም አዲስ አበባ ዮኒቨርስቲ የሙሉ ፕሮፌሰርነት ማዕረግ ሰጥቶታል። የአለ የሥነጥበብና ዲዛይን ትምህርት ቤት የመጀመርያው ሙሉ ፕሮፌሰርሽፕ ማዕረግ መሆኑ ነው።” ሲል አያይዞ የእንኳን ደስ አለህ መልዕክቱን እስተላልፏል። #ደራሲእንዳለጌታከበደ (ፒኤችዲ) “አሁን የሆንከውን ለመሆን፣ አንተው ራስህ የጻፍከውን ግጥም ኖሮ መገኘትን ይጠይቃል።” ሲል መግቢያ አኑሮ ባጋራውና ራሱ ፕሮፌሰር በቀለ መኮንን በጻፈው ‘ቼ በለው’ በተሰኘው ግጥም እናብቃ፥
ቼ በለው!
ሕይወት ጎዳናው ገጹ ሲለወጥ
በጭነት ታክቶ ጀርባው ሲመለጥ
የእንቅፋት አጽሙ ቋጥኙ ሲገጥ
ሸክም ዘንቦበት ትቢያው ሲላቆጥ
ሲሆን ድጥ በድጥ
ሾህ ጭቃ ቅይጥ
ልብህ አይደንግጥ።
በምኞት ቅዥት በስጋት ርዶ
አይፍረስ ግንቡ ወኔህ ተንዶ
ከቆመው ቆመህ ከንፈር ከመምጠጥ
በተስፋ ፈረስ በልጓም ሸምጥጥ።
አያረጅ የለም አይለዋወጥ
ነገን ተማምነህ በመጓዝ ቁረጥ…
ከሩቅ አልመህ ቅርብ አትርመጥመጥ
ሰግተህ ከምትቆም ስትጋልብ ፍረጥ።
#መምህሩጋሽወርቁ ስለ ፕሮፌሰር በቀለ
መምህር ወርቁ ጎሹ የፕሮፌሰር በቀለ መኮንን አስተማሪ ሲሆኑ የ85 ዓመት ሰውም ናቸው። በቀለ ከወጣትነቱ አንስቶ ህልሙን ለማሳካት ታላቅ ጥረት የሚያደርግ ተማሪዬ ነው ሲሉ በኩራት ምስክርነት ይሰጣሉ። መምህር ወርቁ ጎሹ ቀራጺ በቀለ ከሰዎች ጋር የመግባባት ክህሎትን የታደለ የሚወደውን ሙያ እየሠራ ያለ ብቃት ያለው የሥነ ጥበብ ባለሙያ ነው ሲሉ ይገልጹታል።
ጋሽ ወርቁ 30 ዓመታት አስተምረዋል። በቀለን ሲገልጹት የሚደነቅና የሚከበር ይሉታል። በራሳቸው ጥረት ካደጉት ተርታ ይመድቡታል።
ጋሽ ወርቁ ወደ ኃላ መለስ ብለው የፕሮፌሰር በቀለን የትምህርት አቀባበል ሲያጤኑ የቀን የሌት ጥረት የሚያደርግና የልፋቱን ያገኘ በሚል ያስረዳሉ። ተሰጥዖም የሚታይ ነው ይላሉ።
ዛሬ ፕሮፌሰር መሆኑ ለአገር ትልቅ ኩራት መሆኑንም ነግረውናል።
" የበቀለ ፕሮፌሰር መሆን ለእኔ ብቻ ሳይሆን ለአገር ኩራት ነው። እኔ እንደ አስተማሪው ይህን የምሥራች ስሰማ ደስታዬ ያይላል።እንኳን ደስ ያለህ ልለውም እወዳለሁ። "ሲሉ ለተወዳጅ ሚድያ ምስክርነት ሰጥተዋል።
በቀለ መኮንን፤
በብሔራዊ ትእምርት ፍለጋ ውስጥ
#በተባባሪፕሮፌሰርቴዎድሮስገብሬ
I
ከብረት እስከ ጨርቅ በደረሱ ትይዩ ተቃራኒዎች መካከል ሲያመላልሰን የከረመው በቀለ መኮንን፣ ጥቁር ጤፍ ፈጭቶ--ጥቁር ጤፍ አቡክቶ “በጋገራቸው” ኪነቶች አማካይነት ሊፈትነን “ጤፍና ነጻነት” የሚል ርእስ በሰጠው አዲስ ትርኢት ተገልጧል፡፡ “ጤፍ” እና “ነጻነት”? ጤፍ ገቢር ነው፡፡ ነጻነት ደግሞ ኀልዮ፡፡ ጤፍ ይሰፈራል፤ ይፈጫል፤ ይቦካል፤ ይጋገራል፡፡ ነጻነት ግን በኅሊና ይነደፋል፡፡ ጤፍ እና ነጻነት በነገረ ፍጥረታቸው አይገናኙም፡፡ 'እናስ በምን ተጠየቅ ተዛምደው በአንድ ርእስ ውስጥ በ“እና” ተዳሩ?' የሚል ጠያቂ ከመጣ ምላሹን የሚያገኘው ከትርኢቱ ዐውድ ይሆናል፡፡
በቀለ በትርኢት መግለጫዎቹ በገሀድ እንደሚጠቁመን በአዳዲስ ሥራዎቹ ውስጥ ረቂቁ “ነጻነት” በግዙፉ ጋሻ ውስጥ አድሮ ተጨባጭ ሆኗል፡፡ በእርግጥ ጋሻ የሚመስሉ “እብጠቶች” በበቀለ ዕይታዊ መድበለ ቃላት ውስጥ የሰርክ ጉዳዮች ናቸው፡፡ በቀደሙት ትርኢቶች ውስጥ ጋሻዎች አንድም ቅርጽ ከቅርጽ ተጋጭተው ለሚፈጥሩት “ግብታዊ” ፍቺ ሲባል ይመላለሳሉ፤ አንድም ደግሞ የማረሻን የገነነ ወንዴነት ማስከኛ ሆነው በሚዛን ጠባቂነት (as a feminine energy) ይመጣሉ፡፡ በ“ጤፍና ነጻነት” ነጻነት በጋሻ ውስጥ በማደሩ፣ ጋሻ ከቀደመ ግብሩ የተለየ አዲስና ቋሚ ሚናና ግብር ይዟል ማለት እንችላለን፡፡ አዲስ ግብር ለመያዙ ምስክሩ ይህ ብቻ አይደለም፡፡ በትርኢቱ ውስጥ የሚገጥሙን ጋሻዎች በሙሉ በጤፍ ዱቄት የተገነቡ (የተለሰኑ) ናቸው፡፡ የጋሻዎቹ በጤፍ ዱቄት መገንባት አንድም፣ በትእምርቶቹ መካከል የባሕርይ መጋራት እንዲፈጠር፤ አንድም በኪነቱ ውስጥ ጥንድ ምናብ--ድርብ አስተማስሎ (double representation) እንዲከሰት ዕድል ሰጥቷል፡፡ የጉዳዮች በአንድ ወደተሸረቡ መንታ ትእምርትነት ማደግ ተመልካች ሐሳቡን የሚያሰላበትን፣ ትችቱን የሚያፍታታበትን ምቹ የመፈከሪያ ዐውድ እንዲያገኝ አስችሎታል፡፡
ጋሻ የነጻነት እና የአርበኝነት ማኅደር ነው፡፡ (ይህ ዓይነቱ የጋሻ ፍቺ በተገኘበት ባህል ውስጥ ጭምር ይታወቃል፡፡) ቆየት አድርጌ በስፋት እንደማሳየው ጤፍ በፈንታው የ“ኢትዮጵያ” እና “የኢትዮጵያዊነት” ብሔራዊ ትእምርት ነው፡፡ በዚህ ዐውድ የብሔራዊ ትእምርት ፋይዳ አንድም፣ በነጻነት፣ በአገር እና በብሔራዊ ምንትነት መካከል ያለውን ረቂት ተራክቦና ውስብስብ ተጻምሮ ተጨባጭ ማድረግ ነው፡፡ አንድም ደግሞ ተራክቦውን--ተጻምሮውን ጠብቆ ለማኖር ዜጎች በአርበኝነት መንፈስ የሚከፍሉትን የላብና የደም መስዋዕትነት ማመልከት ነው ማለት እንችላለን፡፡ (በ“Gluten-free-dom II” እንጀራ የጠመጠመ ጋሻ በአናታቸው የደፉ፣ በትኩስ የአመድ ደለል ላይ/ውስጥ የቆሙ ሰባት እናቶች እንዲህ ላለው አንድምታ አስረጂዎች ይሆኑናል፡፡)
II
ብሔራዊ ትእምርቶች የብሔራዊ ምንትነት ግላጼዎች (identity expressions) ናቸው፡፡ የምንትነቱ ሥሪት (identity construction) በተረኮቹና በትእምርቶቹ ጥራትና ጥንካሬ ላይ ይወሰናል፡፡ ግላጼዎቹ እና ሥሪቱ የሚተጋገዙ ብቻ ሳይሆን የሚተካኩ ጉዳዮች ጭምር ናቸው፡፡ ያንዱ መድከም ሌላውን ያጎድላል፡፡ ያንዱ መዛል ሌላውን ያፈርሳል፡፡ የብሔራዊ ትእምርት ቀረጻ ብሔራዊ-ጥበባዊ ተልእኮ ነው፡፡ የአንድ ሕዝብ ብሔራዊ ምንትነት በአንጻራዊነት ለዘመናት ጸንቶ ይዘልቅ ዘንድ ተረኮች (ቃላዊ፣ ዕይታዊ፣ ትውናዊ፣ ወዘተ. ተረኮች) እና ትእምርቶች በጥንቃቄ መመረጥና መቀናበር፣ በየጊዜው እየተመረመሩ መታረምና መከለስ ይኖርባቸዋል፡፡ ብሔራዊ ምንትነት በዐቢይነት የውክልና ጉዳይ ነው፡፡ በአንድ አገር ውስጥ እያሉ እንደሌሉ የተቆጠሩ ወገኖች፣ ቸል የተባሉ ሰብአዊ ዕሤቶች፤ አቅም ባገኙ፣ የኃይል ሚዛን በለወጡ ጊዜ በነባር ተረኮች እና ትእምርቶች የተሸመነውን ብሔራዊ ምንትነት እስከ መሻር፣ አፍርሶ እንደ አዲስ እስከመሥራት የሚያደርስ ጥያቄ ያነሳሉ፡፡ ይህ ሲከሰት የአገር ግንባታ ሂደት ይስተጓጎላል፤ ማኅበራዊ ውጥረት ይነግሣል፡፡ (የዛሬዋ ኢትዮጵያ ለዚህ ዓይነቱ እውነታ አብነታችን ናት፡፡) በመሆኑም ብሔራዊ ትእምርት ቢያንስ ቢያንስ ረጅም የታሪክ ዘመንን፣ ሰፊ መልክአ ምድርን እና ገሀድ የወጡ የማኅበረሰብ ክፍሎችን እና ዕሤቶችን ሊያካልል ይገባል፡፡ ብሔራዊ ትእምርት ከውክልናው ፈርጀ ብዙነት ባሻገር በኪነት ከፍታው እና በኀልዮ ጥራቱም ተለይቶ መታወቅ አለበት፡፡ ጥቅል በሆነ አነጋገር፣ ብሔራዊ ትእምርት ጥልቅ በሆነ ጊዜ ውስጥ፣ ጽኑእ በሆነ መሠረት ላይ የሚታነጽ በነባርና በአዳዲስ ዕሤቶች ትብብር የሚሸመን ዐውራ ምስል ነው፡፡
እንደ ኢትዮጵያ ላለ ኅብረ ባህላዊ አገር ብሔራዊ ትእምርት በትግግዝ የሚፈጸም ብሔራዊ--ኪናዊ ተልእኮ ነው፡፡ ብሔራዊ ትእምርት እርስ በርስ ሊናበቡና ሊከታተሉ በሚችሉ በግለሰብ፣ በቡድን፣ በትውልድ በሚፈጠሩ ገባር ምናቦች ትግግዝ በዘመናት ሂደት ምልዓት ላይ የሚደርስ ዐውራ ትእምርት ነው፡፡ እንዲህ ዓይነቱን ኪናዊ ትግግዝ--የምናብ ተናባቢነትና የምስል ተከታታይነት--በተጨባጭ ለማሳየት “ጤፍና ነጻነት”ን በሁለት መንገዶች ማንጸር እንችላለን፡፡ ቀዳሚው መንገድ ይህንን ትርኢት ከበቀለ መኮንን ነባር ትርኢቶች ጋራ እያመሳከሩ መፈከር ሲሆን፤ ተከታዩ ደግሞ በየትኛውም የኪነት ዘርፍ ካሉ ዘመነኞቹ ጋራ--ለምሳሌ ከአዳም ረታ ጋራ--እያናበቡ ማስተሳሰር ነው፡፡ የበቀለ መኮንንን ዕይታዊ ጥበብ ከአዳም ረታ ቃላዊ ኪነት አናብቦ በብሔራዊ ትእምርትነት ለማስላት በቂ ምክንያቶች አሉ፡፡ ለዛሬው ትርኢት የነፍስ ያህል የሆነውን ዐውራ መባያ[1]--ጤፍን በበቀለ የአከያየን ልማድ ውስጥ ከገነነው፣ ከማረሻ ጋራ አስተሳስሮ ለማሰብም እንዲሁ፡፡ ከምክንያቶቹ ውስጥ መሠረታዊዎቹ፡- አንደኛ፣ የዐውድ ተዛማጅነት፤ ሁለተኛ፣ የኀልዮ (የጭብጥ) ተከታታይነት፤ ሦስተኛ፣ የቅኝት ወይንም (የርእዮተ ዓለም) ተወራራሽነት፤ አራተኛ፣ የጊዜ ጥልቀት (የነገረ ፍጥረት ብሉይነት)፤ አምስተኛ፣ ሥነ ልሳናዊ ተዛማችነት ናቸው፡፡
“ማረሻ” የግብርና ማምረቻ መሣሪያ፣ “ጤፍ” ደግሞ የግብርና ምርት በመሆናቸው በተፈጥሮ የቅደም-ተከተል ዝምድና አላቸው፡፡ (ተፈጥሯዊው ቅደም ተከተል በጉዳዮቹ መካከል አለ ያልነውን የጭብጥ ተከታታይነት እና የትእምርት ተጋጋዥነት ተጨባጭ ያደርግልናል፡፡) የማምረቻ መሣሪያው (ማረሻ)፣ የአምራቹ (ገበሬ) እና የምርቱ (ጤፍ) ተፈጥሯዊ የተራክቦ ዐውድ ገጠር ነው፡፡ ጤፍ እና ማረሻ ከ85 ከመቶ በላይ ኢትዮጵያዊ ይኖርበታል የሚባለውን፤ ዳሩ ግን በአገሪቱ ፖለቲካዊ፣ ማኅበራዊ እና ምጣኔ ሀብታዊ እንቅስቃሴ ውስጥ ተገቢ ሥፍራ የተነፈገውን ወገን በቀጥታ ይመለከታሉ፡፡ ከያኒው ለተገፉ፣ ሥፍራ ለተነፈጉ ብሔራዊ ጉዳዮች ማድላቱ የትእምርቶቹን ምርጫ ተገቢነት ከማረጋገጡ ባሻገር ቅኝቱን ርእዮተ ዓለማዊ ያደርገዋል፤ (“history from below” እንደሚባለው)፡፡ ገጠርን አትኩሮ፣ ነባር የግብርና መሣሪያንና ጥንታዊ ምርትን (ማረሻንና ጤፍን) ከዚያው ዐውድ መልምሎ በምናብ ማጥለቁ፣ በምስል ማበልጸጉ እና በኀልዮ ማራቀቁ ብዙኃኑን የሚወክል፣ ዘመናትን የሚዋጅ ጽኑእ ብሔራዊ ትእምርት ለመቅረጽ ዕድል የሚሰጥ ይመስለኛል፡፡
የጤፍ ነገረ ኪን እና ፖለቲካም (the poetics and politics of teff) በቅኝት ከዚህ የሚለይ አይመስለኝም፡፡ ጤፍ በመጠን በአነስተኛነቱ “ዝነኛ” ነው፡፡ ለምሳሌ፣ አንድ የስንዴ ቅንጣት በአማካይ ከአንድ መቶ ሃምሳ የጤፍ ቅንጣቶች ጋራ እኩል እንደሆነ ይገመታል፡፡ ይህ ደግሞ “ከትውልድ ሥፍራው” አልፎ በዓለም ካሉ የእኽል ዝርያዎች በሙሉ በመጠን ትንሹ ያደርገዋል፡፡ በደስታ ተክለ ወልድ መዝገበ ቃላት ይህ የእኽል ዘር በተከታዩ መንገድ ተበይኖ እንመለከታለን፤ “ጤፍ፤ የታናሽ እኽል ስም፤ የሣር ዐይነት ሙርዬ የሚመስል፡፡ (ተረት)፤ ሳይቸግር ጤፍ ብድር” (19962፡ 675)፡፡[2] በዓለም ምግብ ድርጅት ገጽ ላይ ሰፍሮ እንደምናነበው፣ ጤፍ ከኢትዮጵያ ውጪ ባሉ አገራት፣ ለምሳሌ በደቡብ አፍሪካ እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ ከከብቶች ቀለብነት ባለፈ የአፈር መሸርሸርንና የውሃ ብክነትን ለመቀነስ ታስቦ የሚለማ “ተራ ሣር” ነበር፡፡[3] ተወዳጅ ነው በሚባልባት እናት አገሩም ቢሆን በመጠን ማነሱን ታክከው የሚቀርቡ ንጽጽሮች አጓጉልነት አላጣቸውም፡፡ ለአብነት፣ “ከመጤፍ አልቆጠረኝም” እና “ሰው ጤፉ” የሚሉ አገላለጾች በደረጃ ማነስን በገሀድ ያውጃሉ፡፡
ጤፍ በጄኔቲካዊ አወቃቀሩ እጅግ የተወሳሰበ፣ በጾታ ቅንብሩ የተደባለቀ (ፈናፍንት)፣ በምግብ ይዘቱ የበለጸገ የእኽል ዓይነት እንደሆነ የአዝርእት ባለሙያዎች ያስረዳሉ (ሰይፉ 1997)[4]፡፡ ሰይፉ ከተማ በመስኩ ላይ የተካሄዱ ምርምሮችን በከለሱበት ጽሑፋቸው እንደሚያስረዱን፣ የጤፍን የትውልድ ቦታ በእርግጠኝነት መናገር ቢከብድም፣ ጄኔቲካዊ ብዝኃነቱን በማጤን ኢትዮጵያ እናት ምድሩ ልትሆን እንደምትችል መገመት አስቸጋሪ አይሆንም፤ “[T]he genetic diversity for teff exists nowhere in the world except in Ethiopia, indicates that tef originated and was domesticated in Ethiopia” (12)፡፡ ጤፍ በዓለም አቀፍ ደረጃ እጅግ ጥንታዊ ከሚባሉ ጥቂት የእኽል ዘሮች መካከል አንዱ ነው፡፡ በዚህ የእኽል ዘር ላይ ከተካሄዱ ምርምሮች መካከል ብዙዎቹ፣ Nicolai Vavilovን (1951)[5] መሠረት በማድረግ፣ ቅድመ ክርስቶስ ከ4000–1000 በኢትዮጵያ ውስጥ እንደበቀለና ተስፋፍቶ እንደለመደ ይገምታሉ፡፡ እንደ ጤፉ ሁሉ፣ “ኢትዮጵያዊው” ማረሻ፣ ከዕድሜው ጥንትነት ባለፈ ልደትና ዕድገቱም እዚሁ መሆኑን የሚያመላክቱ ምርምሮች አሉ፤ ለምሳሌ፣ Hubert Cochet ኢትዮጵያውያን ገበሬዎች በማረሻ ለ2000 ዓመታት እንዳረሱ ይጠቁማል (2011፡ 31)፡፡[6]
በኢትዮጵያ ውስጥ ከሦስት ሺህ በላይ ዘመናትን ያስቆጠረው፣ ከአገሪቱ ሕዝብ መካከል 70 ከመቶው በእንጀራ መልክ ይመገበዋል ተብሎ የሚገመተው ጤፍ (ታደሠ 2017፡ 50) በሦስቱ ዐበይት የሥነ ልሳን ቡድኖች ተቀራራቢ ስያሜም አለው፡፡ በአማርኛ “ጤፍ”፣ በኦሮምኛ “tafi” በትግሪኛ “ጣፍ”፡፡ በቀለም ስርጭትም ረገድ ወተት ከመሰለ ነጭ (ማኛ) አንስቶ እስከ ጥቁር ድረስ የሚዘልቁ አራትና አምስት ቀለማትን ያቅፋል (አዳም በሁሉም ቀለሞች የሚጫወት ሲሆን የበቀለ ምርጫ ጥቁሩ ነው)፡፡ እንዲህ ያለው የባሕርይ ውስብስብነት፣ የጾታ መንታነት፣ ኅብረ ቀለማዊነት ጤፍን--በአዳም ረታ ጥበበ ቃላት እና በበቀለ ዕይታዊ ጥበብ--ውስጥ ለብሔራዊ ትእምርትነት የተመቸ መባያ አድርጎታል፡፡ “ማረሻ” በበኩሉ ኢትዮጵያውያን የወል ምንትነታቸውን ከሚቀርጹባቸው ብሉይ ዕሤቶች መካከል አንደኛው ነው፡፡ የወልነቱን በዐበይቱ የኢትዮጵያ ቋንቋዎች ውስጥ ባለው የስያሜ ተወራራሽነት መረዳቱ አያሰቸግርም (የአማርኛው “ማረሻ”-- በግእዝ “ማሕረስ”፣ በኦሮምኛ “maarashaa”፣ በትግርኛ “ማሕረሻ” የሚሉ አቻዎች አሉት)፡፡ ብሉይ ነው ስል አንድም፣ የዘፍጥረቱን ጥንታዊነት፤ አንድም፣ የጊዜ ጥልቀቱን ታክኮ የሚመሠረተውን ባህል ጽኑእነት ማመልከቴ ነው፡፡ በተፈጥሮው ቀጥ ያለው፣ የተሳለውና የሾለው ማረሻ፣ በበቀለ ትርኢቶች ውስጥ በከያኒው ፈቃድ፣ ፍላጎትና እጅ መዋቅሩ ተናግቶ፣ “ተፈጥሮው” ተዛብቶ ልክ እንደ ጤፍ ወደ ፈናፍንትነት ተቀይሯል፡፡ የበቀለ ማረሻዎች መዋቅር መናጋት የአድሏዊው የተባዕትነት ሥርዓት ፈርሶ በአዲስ ተምኔታዊ ሥርዓት የመተካቱ አምሳያ ነው፡፡ ከዚህ ሥርዓት ውስጥ ነው እንግዲህ ከያኒው አዳዲስና ነባር ዕሤቶች ተዳርተው የሚሰናኙበትን ብሔራዊ ትእምርት ለመፍጠር የሚታገለው፡፡[7]
ጤፍ እና ማረሻ ኢትዮጵያውያን ጥልቅ ከሆነ ጊዜ፣ የጋራ ታሪካቸውን፣ ርእዮታቸውንና ንጽረታቸውን የሚጠልቁባቸው፤ ሩቅ ከሚባል ትናንት የወል ልቡናቸውንና ምንትነታቸውን የሚያደሩባቸው “ቁሳዊ” ዕሤቶች ናቸው፡፡ ቤኔዲክት አንደርሰን፣ “It is the magic of nationalism to turn chance into destiny” (1983፡ 12)[8] እንዳለው ዕጣ ፈንታቸው ጭምር ተጠላልፎ የተሰናኘባቸው የወል ዕሤቶች፡፡ ማን ከዕጣው ማምለጥ ይቻለዋል? እንደሚታወቀው እንዲህ ያለ ዕሤት በጥልቅ ጊዜ እና በጽኑእ መሠረት ላይ የሚቆም አገር ለማነጽ ምቹ ዕድል ይፈጥራል፡፡ በእርግጥ አንድ ማኅበር በጽናት ይቆም ዘንድ ዕጣውን ከቋጠረበት ሩቅ ትናንት በተጨማሪ፣ በገነነ “የሕዝብ ማኅበራዊ ልቡና” ነገውን የሚዋጅበት የጋራ ስኬት እንደሚያስፈልገው አሌ አይባልም፡፡ ለዚህ ዓይነቱ ስኬት ጤፍ እንግዳ አይመስለኝም፡፡ ትናንት፣ ጤፍን ለሰው ልጅ ምግብነት በማዋል ረገድ ኢትዮጵያ ከዓለም ብቸኛ አገር ነበረች፡፡ ዛሬ፣ በተለይ በአውሮፓና በሰሜን አሜሪካ በሚኖሩ፣ እንጀራን መለያቸው ባደረጉ በ“ነባሬ ባዕድ”[9] (diaspora) ኢትዮጵያውያን በሚተዳደሩ ምግብ ቤቶች አማካይነት ዝናን ያተረፈው ይህ የእኽል ዘር የኢትዮጵያን ድንበር ተሻግሯል፡፡ በጣዕሙ፣ በምግብ ይዘቱና ለጤና ባለው ጠቀሜታ ከተመጋቢው እኩል በሥነ ምግብ ተመራማሪዎች ዘንድ ተወዳጅ የሆነው ጤፍ በትልልቆቹ የዓለም የመገናኛ ብዙኋን ሳይቀር (ለምሳሌ፣ በBBC, VoA, The Washington Post, The Guardian, The New York Times, ወዘተ.) “the next ‘super grain’ of the World” የሚል መወድስ ወርዶለታል፡፡ ይህንን ዝና ተከትሎ ሊመጣ የሚችለው ማኅበራዊ ከፍታ እና ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ--(as a national branding) ብሔራዊ ክብርና ኩራትን የመፍጠር አቅም አለው፡፡ የጤፍ ታሪካዊ፣ ባህላዊ እና ማኅበረ-ኢኮኖሚያዊ ፋይዳው አንድም በመከባበር ላይ የተመሠረተ አንድነትን ለመፍጠር የሚያግዝ፤ አንድም በጎሣ፣ በሃይማኖት እና በቋንቋ ምክንያቶች የተፈረቀቀውን ብሔራዊ ልቡና (the national psyche) ለማከም የሚያስችል ዕድል እመስጠቱ ላይ ነው፡፡[10]
III
ትኩረታችንን ወደ ዛሬው ትርኢት እንመልስ፡፡ “ጤፍና ነጻነት”፡፡ ጤፍ የ“ኢትዮጵያ” እና “የኢትዮጵያዊነት” ብሔራዊ ትእምርት፤ ጋሻ በበኩሉ የነጻነት እና የአርበኝነት ማኅደር መሆኑን በመግቢያዬ አመልክቻለሁ፡፡ እንዲህ ያለው የጋሻ ትርጉም ህልው በሆነበት ባህል ውስጥ ጭምር ታውቆ የሚሠራበት ነው፡፡ በትርኢቱ ውስጥ ከቀረቡት ሥራዎች ብዙዎቹ ከጤፍ እና ከጋሻ ተራክቦ የተገኙ ናቸው፡፡ ይህ ማለት ግን ሁለቱ ጉዳዮች በሁሉም ትዕይንቶች ውስጥ እኩል ሥፍራ አላቸው ማለት አይደለም፤ በፍጹም፡፡ ጤፍ በሚናው ይልቃል፡፡ የጭብጥ ክትትል ከመፍጠር፣ የመተርጎሚያ ዐውድ ከመተለም ባለፍ ዝርው ህልውናም አለው፡፡ ጤፍ በቤት ውስጥ ቁስነት ተከስቷል፤ የግድግዳ ምርጊት ሆኖ ተገልጧል፤ ወዘተ፡፡ ጤፍ ታሪክ ነው፤ ምጣኔ ሀብት ነው፤ ፖለቲካ ነው፤ ርእዮተ ዓለም ነው፡፡ በጤፍ የሰው አካል ተገንብቷል፤ የሰው ገጽ ተነድፏል፡፡ ገጻተ ሰብኡ ከጤፍ መልኩንም ይዘቱንም ወርሰዋልና ወደ ጤፍነት ተለወጡ ማለትም እንችላለን፡፡ ከተጨባጭ ሁነቶችና ህልውናዎች ባለፈ ጤፍ ለልእለ አካላዊ ክስተቶች ማድሪያነት ውሎም እንመለከታለን፡፡ ለምሳሌ፣ “ጓዳና ግርግዳ” የሚል ርእስ በተሰጠው፣ በቀጫጭን ዘንጎችና በጥቁር ጤፍ ትግግዝ በተቀናበረ ግድግዳ ላይ (በጤፍ ቡኮ የተመረገ፣ ጋሻ ያዘለ ግድግዳ) ከያኒው ይሁነኝ ብሎ በተዋቸው ሽንትር ሽንቁሮች ውስጥ አሳልፈን የምናየው “የቤተ ክርስቲያን” ጨርቅ ልእለ ፍጥረት ህላዌ ከልደትና ሞት ጋራ የታተመበት ነው፡፡ በመሆኑም ጤፍ በትርኢቱ ውስጥ የነገረ ሰብእን ዕጣ የምናሰላበትን ስብርባሪ አፍታ ጭምር ይሰጠናል ማለት ነው፡፡
በትርኢቱ ውስጥ በጤፍ ከተገነቡ ምስሎች መካከል ገጸ ሰብእ[11] የተነደፈው በሁለት ተከታታይ ትዕይንቶች ውስጥ ብቻ ነው፤ በ“Gluten-free-dom I” እና በ“Gluten-free-dom II”፡፡ እነዚህ ትዕይንቶች “ተከታታይ” ብለን ብቻ የምናልፋቸው አይመስሉኝም፡፡ ይልቁንም እጅግ በተወሳሰበ ትእምርታዊነትና በተራቀቀ ዘይቤ የተከየኑ፣ ለፈርጀ ብዙ ንጽጽርና ትርጓሜ የተመቹ ወደረኛ ቅርጾች ናቸው፡፡ ኋለኛውን መነሻ እናድርግ፡፡ ጀርባ ለጀርባ እንጂ ፊት ለፊት የማይተያዩ፣ ትከሻ ለትከሻ ገጥመው ክብ የሰሩ የሰባት ነፍሰ ጡሮች ትዕይንት ነው፡፡ በዚህ ትዕይንት ውስጥ ሴቶቹ ክብነቱን ጠብቆ በጠባቡ በሚዞራቸው ቡላ ቀለም ያለው የአመድ ደለል ላይ ቆመዋል፡፡ ደለሉን ተከትሎ በክቡ የሰፈነው ነጭ አመድ ከሸማ የተሠራ ምንጣፍ፣ በዙሪያው የተኮለኮለው የከሰል ሰልፈኛ ደግሞ ጥቁር ጥለት ይመስላሉ፡፡ በሆዳቸው ፍሬ የያዙ ሰባት ሴቶች የተደራረቡ እጆቻቸውን ሐፍረታቸው ላይ ጣል እንዳደረጉ፣ እንጀራ የለበሰ ጋሻ አናታቸው ላይ እንደደፉ፣ በአክብሮት ይሁን በፍርሐት አልያም በሐፍረት አቀርቅረዋል፡፡
ሁለተኛው ትዕይንት የአንድ ሰው “ገድል” ነው፡፡ ይህንን ገድል እኔ “ገልና ገልቱ” ብዬ እጠራዋለሁ፡፡ (“ገል” የጋን ስባሪ፤ “ገልቱ” ያልሠለጠነ፣ በድንቁርና የተደፈነ፡፡) ዙሪያውን በተሰባበሩ ሸክላዎች የተከበበ፣ ከምድር ከፍ ብሎ የታነጸ፣ ባለ ስድስት ማዕዘን ቅርጽ ያለው ጡብ ገዝፎ ይታያል፡፡ ሙቀት ፍለጋ እጆቹን ወደ ፊት የዘረጋው ሰው እጡቡ አናት ላይ ባፍጢሙ እደፋው የአባቶቹ ጋሻ ላይ “ተመቻችቶ” ተቀምጦ “የደቀቁ የሸክላ ገሎችን በተመስጦ ይሞቃል”፡፡ ሁለቱ ትይዕንቶች የመከታተል ብቻ ሳይሆን እርስ በእርስ የመተረጓጎም ባሕርይም አላቸው፡፡ ይህንን ለማጤን እላይ በገለጻዎቹ ውስጥ የሰፈሩትን ወደረኛ ድርጊቶችና ሁነቶች ማነጻጸሩ ብቻ በቂ ይመስለኛል፡፡
ሴቶቹ በገዛ ፈቃዳቸው ፋታ ለማይሰጥ፣ ድካም ለበረታበት፣ ህመም ላለበት ኃላፊነት ራሳቸውን የሞሸሩ ይመስላሉ፡፡ አንድም የቁጥራቸው ሰባትነት የኃላፊነቱን ክብደት ያጸናል፡፡ ሰባት ቁጥር በትውፊት፣ በሃይማኖት፣ በኪነት፣ ወዘተ. ውስጥ ምልዐትን፣ ፍጹምነትን ለማመልከት ተመላልሶ የሚመጣ ነባር መባያ ነው፡፡ ፍጹምነቱና ሙሉነቱ የበረከትም የቅጣትም ሊሆን ቢችልም፡፡ አንድም ሴቶቹ የቆሙበት የአመድ ደለልም ሆነ አካላቸው ተገጣጥሞ የፈጠረው የቅርጽ ክብነት እላይ በቁጥር ጸና ያልነውን በድካምና በህመም የተሞላ ኃላፊነት ፍጹም ያደርገዋል፡፡ በክብነት ውስጥ መውጫ ቀዳዳ ይጠፋል፤ መነሻና መድረሻ ይታጣል፡፡ ለእረፍት የሚሆን ጥጋት አይሰጥም፡፡ በቀለ በምስሉ መግለጫ ላይ በገሀድ እንደሚጠቁመን ሰባቱ ሴቶች በዝርው ሰባቱን ቀናት ይወክላሉ፡፡ በዚህም ሰንበት ተገድፏል፤ የለመድነው የጊዜ መስፈሪያ ተሽሯል፡፡ ቀናቱ በሴቶቹ ድርጊት ተቃኝተው “ጊዜ” ከሰው ጋራ የሚለያይበት መስመር ደብዝዟል፡፡ መነሻ፣ ማጋመሻ፣ መዳረሻ የሚባሉ አንድም፣ የድርጊትና የሁነትና መሥፈሪያዎች፤ አንድም የጊዜ ዋቢዎች ሳስተዋል፡፡
እላይ በእንጥልጥል ወደተውነው ጉዳይ እንመለስ፤ “ገሎችን መሞቅ” ምን ማለት ነው? ከከያኒው ምስክርነት ባሻገር የወጣቱ የእጅ አዘረጋግ ሁኔታ በሙቀቱና በአካሉ መካከል በፈጠረው ሚዛን ሙቀትና ምቾት መኖራቸውን እንረዳለን፡፡ ግን እሳቱ ወዴት ነው? የሙቀቱ ምንጭስ ምንድ ነው? ለእነዚህ ጥያቄዎች በአንድምታ የምንገልጠው እውነታ ካልሆነ በቀር፤ በቀጥታ የምናገኘው መልስ ያለ አይመስለኝም፡፡ በባለ ስድስቱ ማዕዘን ጡብ ዙሪያ በሰፊው የፈሰሱት የገል ስብርባሪዎች በኢትዮጵያውን የቆየ ታሪክ ውስጥ ቋሚ ሥፍራ ያላቸው፣ በሸክላ የተሠሩ አገረ ሰብአዊ ዕደ ጥበባት ናቸው፤ በየዓይነቱ --የጀበና፣ የምጣድ፣ የድስት፣ የጋን፣ የጣባ፣ የዕጣን ማጨሻ፣ ወዘተ. ስብርባሪዎች፡፡ ስብርባሪዎቹን በቅርበት ላጤነ ሰው ዕደ ጥበባቱ በእርጅና ምክንያት ከሰርክ ግብራቸው የተገለሉ አይመስሉም፡፡ ይልቁንም ከነወዛቸው ከነጉልበታቸው ያሉ፣ ከግብራቸው በግድ ተነቅለው የደቀቁ ነው የሚመስሉት፡፡ በሌላ ቋንቋ ሙቀቱ የሚመነጨው ከገሎቹ ትኩስነት ነው፡፡ ትኩስነት፤ አንድም፣ ከእሳት ምድጃ የሰበሰቡትን ሙቀት ይዞ ማቆየት ነው፡፡ ገልቱው ዕደ ጥበባቱን ከተሰየሙበት ምድጃ ላይ ነቅሎ --ቡናና ወጡን ደፍቶ፣ ዳቦና እንጀራውን ገልብጦ--ጀበናውን፣ ድስቱን፣ ገበር ምጣዱን፣ ምጣዱን አንክቶ፣ እንካቹን ሜዳ ላይ ዘርቶ ትኩስነታቸውን እየሞቀ ነው፡፡ አንድም በዘይቤ ተራ እንናገርና ትኩስነት አፍላነት ነው፡፡ የአገልግሎት ዘመን አለመጋመስ፡፡ ከብርታትና ጥንካሬ ጋራ መሆን፡፡ ጠላውን ደፍቶ፣ እርጎውን ገልብጦ፣ ወዘተ. ያደቀቃቸው የሸክላ ውጤቶች፡፡
በዚሁ ተጠየቅ ከተጓዝን የሴቶቹን አቋቋም በመመርመር በሰባት ቁጥር እና በክብ ቅርጽ ትግግዝ ጸና ያልነውን ህመም በተጨባጭ መመልከት እንችላለን፡፡ የሴቶቹ ፋታ የለሽነት ድርጊቶቹንና ሁነቶቹን በሙሉ ወደማያቋርጥ ሂደትነት ለውጧቸዋል፡፡ ይህንን ለማጤን--በተለመደው አገላለጽ--እንጀራ የጠመጠመ ጋሻ ከሰፈነበት የራስ ጸጉራቸው፣ በአመድ ደለል እስከተደበቀው የእግር ጥፍራቸው ድረስ መመልከቱ በቂ ነው፡፡ አመዱ እና እንጀራው ትይዩ ናቸው፤ አንዱ ምርት ሌላው ግርድ፡፡ ከአናት እንጀራው በተመረተ ቁጥር ከስር አዲስ አመድ ይወድቃል፡፡ አዲስ አመድ --ትኩሣቱን ያልጨረሰ አመድ፤ ረመጥ፡፡ ይህ ማለት ሴቶቹ ረመጥ ላይ ቆመዋል እንደማለት ነው፡፡
ቀደም አድርጌ ለማሳየት እንደሞከርኩት ሴቶቹ እንዲህ ያለውን በድካምና በህመም የተሞላ ኃላፊነት በፈቃዳቸው መርጠው ተቀብለዋል፡፡ በማሕፀኗ ሽል የያዘችን እናት በረመጥ እስከመድበን የሚያደርስ መስዋዕትነት ምን የሚሉት ኃላፊነት፣ እንዴት ያለ ዓላማና ተልእኮ ነው? የራስን ሰብእና የሚያደቅቅ፣ ህልውናን የሚያመነምን፣ ሕይወትን የሚያሰልል ተግባር ውስጥ በፈቃድ መሳተፍ ራስን ለከፋ ጉዳት ማጨት ይመስላል፡፡ የፈቃድ ጉዳት (self-destruction)፣ ከፍ ሲልም የፈቃድ ሞት ከዳግም ልደት ጋር የሚዛመዱበት እንዲህ ያለው አቀራረብ ሚታዊ አመሳሰል ነው፡፡ ይህን ዓይነቱን አመሳሰል በሚቶሎጂ ውስጥ በብሉየ መዋዕልና[12] ደንብ ከተቀረጹ ምስሎች (archetypal imageries) ጋራ አቆራኝተን መመልከት እንችላለን፡፡ በሆዳቸው ፍሬ የያዙ ሴቶች ትከሻ ለትከሻ ገጥመው ክብ መሥራታቸው፣ በሠሩት ክበብ ውስጥ ረመጥ ላይ መቆማቸው፣ በአመድ ደለል መያዛቸው፣ እንጀራ “ማብቀላቸው” በአንድ ግዜ ኦሮቡረስን (በክብነት) እና ፊኒክስን (በረመጥነት-አመድነት) አቃልጠን እንድናስብ ያደርገናል፡፡ ራሷን አቃጥላ ከትቢያዋ ላይ ነፍስ የምትዘራው ፊኒክስ (Phoenix) እና በክብ ቅርጽ ከጅራቱ አንስቶ ሙሉ አካሉን በልቶ በአዲስ ህልውና የሚከሰተው አሮቡሮስ (Ouroborus) “ሁለንተናዊ” ሊባሉ የሚችሉ የህመምና ድኅነት፣ የሞትና ልደት ትእምርቶች ናቸው፡፡ ባዶ እግራቸውን ረመጥ ላይ የቆሙ ሰባት እናቶች በቸልታ የተጎዳውን ነባር ምንትነት፤ በሆዷቸው የያዟቸው ሰባት ፍሬዎች ደግሞ እንደ አዲስ ይወለድ ዘንድ የሚጠበቀውን ርእይና ርእዮት ይወክላሉ፡፡ ከዚህ ትዕይንት ዓላማዎች መካከል አንዱና ምናልባትም ቀዳሚው ለዘመናት ለኖረው፣ ዳሩ ግን ቸል ለተባለው የእናቶች ህመምና ድካም--የላቀ ብሔራዊ ተግባር--ዕውቅና መስጠት ነው፡፡ ይህ ዕውቅና ልዕለ ሰብአዊ እና ልዕለ ታሪካዊ እንጂ ተርታና ሰርካዊ አይደለም፡፡ በሌላ ቋንቋ፣ ከያኒው ከፍ ባለ የአከያየን ስልትና ርእዮት እናቶችን ጥልቅ ጊዜ ውስጥ በመትከል ወደ ሚታዊ ተጋዳሊነት ቀይሯቸዋል፡፡ በምላሹም ከዚያው ጥልቀት ውስጥ በጽናት የሚቆም ብሔራዊ ትእምርት እና ብሔራዊ ምንትነት ለማስገር ሞክሯል፡፡
አንድም እናቶች ካለመኖር ህጽን መኖርን አስገኝተዋልና ለዚያም ኪናዊ ውዳሴ እንደ ማውረድ ሊቆጠር ይችላል፡፡ በአንዳንዶች ግምት “ጤፍ” የሚለው መጠሪያ “ጠፋ” ከሚለው ቃል የተገኘ ነው፤ ጠፋ፣ መኖር አቆመ፣ ህልውናው አበቃ እንደማለት፡፡ በሌላ ቋንቋ የዚህ የእህል ዘር የመጠን አነስተኛነት ከመኖር ይልቅ ላለመኖር ይቀርባል እንደማለትም ነው፡፡ የ“ጤፍ” የፍቺ ነቅኡ “ጠፋ” የሚለው ግስ ከሆነ፣ አንድም፣ ጤፍ የምንለው፣ በጣት የምንቆነጥረው ደቃቅ ነገር በተጨባጭ አለመኖርን ያስተማስላል (the representation of absence, the visibility of invisibilty) እንደማለት ነው፡፡ አንድም ዐውራውን የብሔራዊ ሚቶች መሻት--የመነሻዎች ሁሉ መነሻ የመሆንን፣ ከምንምነት ነቅእ የመፍለቅን መሻት--ይጠልፍልናል፡፡ ጤፍ አለመኖርን ከወከለ ከጤፍ የምንጠልቀው “ኢትዮጵያዊነት” ከእመ አበ አልቦ እንደተገኘ (creation ex nihilo, that is, creation from nothing) ይቆጠራል፡፡ በዘይቤ ተራ እንነጋገርና የኢትዮጵያ ገበሬ “አለመኖርን” ይዘራል፡፡ እናቶች ደግሞ ከአለመኖር ማሕጸን “እንጀራን” የመሰለ ግዙፍ ኑባሬ ያዋልዳሉ እንደማለት ነው፡፡ ከጤፍ አብራክ እንጀራ የመክፈሉን ጉዳይ፣ እናቶቹ በሆዳቸው ከያዙት ጽንስ መወለድ ጋራ አቆራኝቶ ማየት ይቻላል፤ ያ ጽንስ አንድም በነባርና በአዳዲስ እሴቶች ትብብር ይሸመናል ያልነው “ኢትዮጵያዊነት” (pan-Ethiopianism) ነው፡፡ የእንጀራው አናት ወጥቶ በጋሻ ቅርጽ መስፈኑ ደግሞ የልደቱ መፈጸም ማረጋገጫ ትእምርት ነው፡፡ ጋሻ የአርበኝነትና የነጻነት ትእምርት፤ ጤፍ ደግሞ የኢትዮጵያና የኢትዮጵያዊነት ማደርያ ነው ካልን፣ በጋሻ መልክ የተከሰተው እንጀራ የዚህ ማረጋገጫ ሰንደቁ (the symbol of national imaginary) ይሆናል፡፡ አንድም በጋሻ ቅርጽ አናታቸውን የከበበው እንጀራ በሰማዕትነት እንዳገኙት የብርሃን አክሊል (halo or nimbus) ሊቆጠር ይችላል፡፡ እንዲህ ያለው ሐቲት ለኪነቱ በ“በብሉየ መዋዕልና” ደንብ ኢትዮጵያንና ኢትዮጵያዊነትን አጥልቆ የሚተክልበትን ረቂቅ ዐውድ ይሰጠዋል፡፡
ኢትዮጵያውያን አንጀራን መመገብ የጀመሩበትን ጊዜ የሚያመለክት እርግጠኛ መረጃ የለም፡፡ ነገር ግን የእንጀራን መነሻ የሚጠቁሙ፣ ዘመኑን እስከ ቅድመ ክርስቶስ እስከ 100 ዓ.ዓ.
የሚያደርሱ የቃል ተረኮች እንዳሉ ስትዋርትና አስናቀ ይናገራሉ (1962: 127)[13]፡፡ በእነዚህ ተረኮች ወስጥ እንጀራ ኢትዮጵያውያን በተቸገሩ ወቅት ከልእለ ፍጥረት ህላዌ የተሰጠ በረከት ተደርጎ ነው የሚቀርበው፡፡ (በበቀለ ኪነት ውስጥ ያንን ሚና ወደ ሚታዊ ህልውናነት የተሸጋገሩት እናቶች ወስደውታል):: ቀደም አድርገን የጠቀስነው የታደሠ ጥናት እንደሚያመላክተን (2017፣ 50) ከኢትዮጵያ ሕዝብ ውስጥ 70 ከመቶ ያህሉ ጤፍን በእንጀራ መልክ ተመጋቢ ነው፡፡ ይህ ቁጥር የጤፍ እንጀራን ለብሔራዊ ምግብነት የሚያበቃው ይመስለኛል፡፡
ጋኖቹን[14] አንክቶ፣ ባፍጢሙ እደፋው ጋሻ ላይ ተቀምጦ ስብርባሪ ገሎች እየሞቀ በምቾት የሚመሰጠው ገልቱ በፈንታው ፍቺው የዚህ ተቃራኒ ነው የሚመስለው፡፡ በእኔ አረዳድ ትዕይንቱ የዘመናችን ክፉ አባዜ--አገር ለዘመናት ጸንታ የኖረችባቸውን የዕሤት ሥርዓቶች፣ የጋራ ታሪኮች፣ የወል ልቡናዎች የመቀናቀን አባዜ--በስላቅ የተነደፈበት ነው፡፡ ስላቁ የቤቱን ማገር እየመዘዘ በሚያነድድ፣ መሠረቱን እየቆረቆረ ቤቱን ራሱ ላይ በሚንድ ገልቱ ላይ ቢያርፍም፣ አገራዊ አደጋው የምር እና ቅርብ መሆኑን ትላልቅ ጋኖችን በማውደም አሳይቷል፡፡ አገር ጸናባቸው ያልናቸው ረቂቅ ዕሤቶች ወጣቱን በከበቡት ስብርባሪ ገሎች ገዝፈው ይታያሉ፡፡ “ጋን” ከአገረ ሰብእ ጥበብነቱ ባሻገር አገር አጽንተው ያቆዩትን ረቂቅ ዕሤቶች ለመወከል የሚያበቃ ሥነ ልሳናዊ እና ሥነ ፍቻዊ ባሕርይ አለው፡፡ በተለይም ቃሉ “ጋኖች” ተብሎ በብዙ ቁጥር ሲጠራ የፍቺው ስፋት ከማጀት እስከ አደባባይ ይዘልቃል፤ “ጋኖች፤ ትልልቆች ሰዎች ዋኖች ጨዎች ጎምቱዎች አባቶች ዐዛውንቶች፡፡ (ተረት)፤ ጋኖች ዐለቁና ምንቸቶች ጋን ኾኑ” (ደስታ ተክለ ወልድ፣ 280)፡፡ አንድም፣ ከማጀት እስከ ቤተ መንግሥት የተዘረጋ ፍቺ አለው፤ ከጠላ መጥመቂያ፣ ከጠጅ መጣያ ቁስነት እስከ ንጉሥ መጠሪያት የሚደርስ ፍቺ፤ የጃን ሆይ አቻ ሆኖ፣ “ጋን ሆይ ፤-ገናና ሆይ፤--ጃን ሆይ፡፡” (280) እያስባለ፡፡
እስካሁን ለማሳየት እንደሞከርኩት Gluten-free-dom “I” እና “II” በተወሳሰቡ ትእምርቶች እና በተራቀቁ እይታዊ ሜታፈሮች የተከየኑ ድንቅ ምስሎች ናቸው፡፡ በምስሎቹ መካከል የሚካሄደው ንጽጽር ከዚህም አልፎ ልሄድ ይችላል፡፡ እኛ ይህን በይደር ዘግተን ለመጣጥፉ እንደ ማሳረጊያ ወደሚያገለግሉ አንድ ሁለት ነጥቦች እንለፍ፡፡
IV
በትርኢቱ ውስጥ ከቀረቡት ሥራዎች ብዙዎቹ --ከፀሐይ እና ጎጆ (ከባህል እና ተፈጥሮ ) መስተጋብር ከተቀሰቀሱ የሰርክ ደፋ ቀናዎች (“አሁንና ቅድም” I፣ II፣ III)፣ የዘወትር ስሜቶች (“አዙረኝ አዛዙረኝ”) አንስቶ፤ ረቂቆቹ የወል ዕሤቶች፣ የጋራ ልቡናዎች እስከተከተቡባቸው ምስሎች (“ጓዳና ግድግዳ”፣ Gluten-free-dom “I” እና “II”) ድረስ ከጤፍ እና ከጋሻ ትእምርታዊ ተራክቦ የተገኙ ናቸው፡፡ እርግጥ ነው እንዲህ ካለው የትርኢት ጠቅላይ ፈለግ የሚሸሹ ጥቂት ሥራዎች አይጠፉም፡፡ ለዚህ ደግሞ፣ “የገደል ማሚቶ”፣ “ቆሜ ተቀምጬ” እና “አዲስ ጠላ በሰባራ አንኮላ” አብነት ይሆናሉ፡፡ “የገደል ማሚቶ” ለኀልዮ እምብዛም ያልተጨነቀ፣ ምናልባትም የሄደ ድምጽ ተመልሶ የሚመጣበት የቅርጾች ጨዋታ ነው፡፡ በ“አዲስ ጠላ በሰባራ አንኮላ” ውስጥ የጤፍና የጋሻን የተናጠልም ይሁን የወል ህልውና በገሀድ ፈልገን ስለማናገኝ ሥራው ከትርኢቱ አጠቃላይ መንፈስ ያፈነገጠ ይመስላል፡፡ ይሔ ግምት ግን ኪነቱን ከቀሪዎቹ ሥራዎች ጋራ አናብበን መተርጎም ስንጀምር በቀላሉ የሚፈርስ ነው፡፡ እንዲህ፣ እንደ “ጤፍና ነጻነት” ባለ አንድ ወጥ ርእስ በተሰጠው ከፍ ያለ ትርኢት ውስጥ ሥፍራ ያገኙ፣ በተቀራራቢ የጊዜ ክበብ ውስጥ የተከየኑ ሥራዎች በአመዛኙ ተነጥሎ ከሚከናወን ዝግ ምልከታ ይልቅ ለአጎራባች (co-textual) እና ለዐውዳዊ (contextual) ምርምር ይጋብዛሉ፡፡ ይህንን አጠቃላይ የነገረ ፍካሬ መርህ ከግምት ካስገባን፣ ከያኒው በምስሉ መግለጫ ላይ ባቀረበው ፍቺ ብቻ ረግተን የምንቆም አይመስለኝም፡፡ ይልቁንም በአንድምታ ተጨማሪ ትርጉም ለማከል እንጋበዛለን፡፡ በእኔ እምነት በትርኢቱ ውስጥ በአካል ጭምር የተጎራበቱት Gluten-free-dom “I” እና “አዲስ ጠላ በሰባራ አንኮላ” ከጤፍ እና ጋሻ መጉደል ባሻገር በገሎቻቸው ተሳስበው በመንፈስ ይሰምራሉ፤ በጭብጥ ይከታተላሉ፡፡ በትርጓሜም እንደሚከተለው ይተጋገዛሉ፡፡
በጥንታዊው የሒሳብ ማሰላሰያ፣ በአባከስ አምሳያ የተበጀው በአራት ማዕዘን የብረት ፍሬም የታጠረ ምስል፣ ብረቱ ላይ ሻጥ ሻጥ ተደርገው አግድም የተዘረጉ ወልጋዳ የእንጨት ዘንጎች፣ በዘንጎቹ ላይ የሚንሸራሸሩ በቅርጽ
9 months ago
ስመ ጥሩ የሚድያ ሰው መርዕድ በቀለ በአትላንታ አረፈ
. በደርግ ጊዜ የማስታወቂያ ምክትል ሚኒስትር ነበር
ከዕዝራ እጅጉ (ተወዳጅ ሚድያ)
#ታሪክ በኢትዮጵያን ሄራልድ፣በየዛሬይቱ ኢትዮጵያ ጋዜጦች፣እንዲሁም በኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት በመምሪያ ኃላፊነት ያገለገለው አቶ መርዕድ በቀለ ትናንት ህዳር 4 2018 በአትላንታ ህይወቱ ማለፉ ተሰምቷል።
የደርግ ዘመን ማብቂያ ላይ የማስታወቂያ ምክትል ሚኒስትር የነበረው የሚድያ ሰው አቶ መርዕድ በሥነ ፅሁፍ ችሎታው የተመሠከረለት ነበር። የሕይወት ታሪኩ የአማርኛ ኢንሳይክሎፒዲያ "መዝገበ አእምሮ ቅፅ ሁለት ላይ የሰፈረለት አቶ መርዕድ በቀለ በ2016 በተደረገው የክብር ሽልማት የህይወት ዘመን ተሸላሚዎች ከእጩዎቹ አንዱ ነበር።
አቶ መርዕድ ተወዳጅ ሚድያ የሚያከናውናቸውን የስነዳ ሥራዎች የሚደግፍ ፣ የሚያበረታታ የቅርብ ሰው ሲሆን በህልፈቱም የተሰማንን ሀዘን እንገልጻለን። የካቲት 26 2018 ሲመጣ 80 ዓመቱን ይይዝ የነበረው አቶ መርዕድ ከሰዎች ጋር በቀላሉ የሚግባባ እና የፅሑፍ ሥራንም በጥንቃቄ የሚያከናውን ነበር። እኛም የህይወት ታሪኩን እንደሚከተለው እናቀርባለን።
ትውልድ እና ልጅነት
መርዕድ በቀለ በ1938 ዓ.ም. የካቲት 26 ቀን አዲስ አበባ ቀጨኔ መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን አካባቢ ተወለደ። አባቱ አቶ በቀለ ወ/ኪዳን የአብነት ትምህርት ቤት ገብቶ የቤተ ክርስቲያን ትምህርት እንዲማር ፍላጎቱ ቢኖራቸውም፣ እናቱ ወ/ሮ ጽጌ ወርቅ ተክለ ጻዲቅ ግን ልጃቸው ከአጠገባቸው እንዳይርቅ በማሰብ በቤት ውስጥ መምህር ቀጥረው ፊደል ከቆጠረ በኋላ በአካባቢው በነበረው የየኔታ ትምህርት ቤት ገባ።
ትምህርት
በኋላም በአምኃ ደስታ የአንደኛ፣ በዳግማዊ ምኒልክ ትምህርት ቤት ደግሞ የኹለተኛ ደረጃ ትምህርቱን አጠናቀቀ። አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ገብቶ በውጭ ቋንቋዎች እና ሥነጽሑፍ በእንግሊዘኛ ቋንቋ በ1965 ዓ.ም. ተመረቀ።
ወደ ሥራ ዓለም
በዚያው ዓመት ነበር በቀድሞው ልዩ ካቢኔ ቢሮ በታላቁ ቤተመንግሥት ውስጥ የተቀጠረው። ልዩ ካቢኔ በነበረበት ወቅትም ዋና ሥራው ከተለያዩ የዓለም ዜና ምንጮች (Reuters, AFP, BBC… ወዘተ) ከሚሠራጩ ዜናዎች ውስጥ የተመረጡትን እየተረጎመ በአለቃው በኩል ለንጉሡ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ማቅረብ ነበር። ሆኖም በዚህ ሥራ ከሦስት ሳምንት በላይ አልዘለለም።
በወቅቱ የማስታወቂያ ሚኒስቴር ለኢትዮጵያን ሄራልድ እንግሊዘኛ ጋዜጣ የሪፖርተር ቅጥር ያወጣውን ፈተና አልፎ፥ የማታ ኤዲተር ሆኖ ሥራ ጀመረ። ብዙም ሳይቆይ ወደ ቀን ተዘዋወረ።
የህትመት ሚድያ
መርዕድ በ1967 ዓ.ም. ባገኘው የትምህርት ዕድል ወደ ሞስኮ አቅንቶ ነበር። በዚያም ለአንድ ዓመት ስለ ሶሻሊዝም ፅንሰ ሐሳብ ካጠና በኋላ ወደ አገሩ ተመልሶ በዚያው በኢትዮጵያን ሄራልድ በአዘጋጅነት ለተወሰኑ ዓመታት አገልግሏል። ቀጥሎም ወደ “የዛሬይቱ ኢትዮጵያ” ጋዜጣ በዋና አዘጋጅነት ዕድገት አግኝቶ እንዲሠራ ተደረገ። ብዙም ሳይቆይ ወደ አዲስ ዘመን ዕለታዊ ጋዜጣ በዕድገት ተዛውሮ በምክትል ዋና አዘጅነት ለኹለት ዓመታት ከሠራ በኋላ ዋና አዘጋጅ ሆኖ እንዲሠራ ተመደበ።
ከኢዜአ እስከ ምክትል ሚኒስትር
በሥራው ባሕርይ የተነሣ መርዕድ በተደጋጋሚ ‘‘ለጥያቄ ትፈለጋለህ’’ እየተባለ ወደ ደርግ ጽሕፈት ቤት ይጠራ ነበር። እንደ እኤአ 1975/76 ሁለት የደኅንነት ሰዎች ከመሥሪያ ቤቱ መጥተው ወደ ማዕከላዊ እስር ቤት ወሰዱት። ሁኔታው ነገሩ ለሕይወቱ እንደሚያሰጋው በመገንዘብ ከቦታው እንዲዛወር አለቃው የነበረውን ደራሲ በዓሉ ግርማን ደጋግሞ ይጠይቅ፣ ይወተውትም ጀመር። ውትወታው ተቀባይነት አግኝቶ በዕድገት የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ሐላፊ ሆኖ ተዛወረ፡፡ እዚያ ለአንድ ዓመት እንደቆየ፥ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት መምሪያ ሐላፊ ሆኖ እንዲሠራ ተመደበ። ለኹለት ዓመታት ካገለገለ በኋላ፥ ከሀገር እስከወጣበት ጊዜ ድረስ የማስታወቂያ ምክትል ሚኒስትር ሆኖ አገልግሏል።
አበርክቶ
መርዕድ በሥራ ላይ በነበረበት ጊዜ በተለያዩ ዓለም አቀፍና አህጉራዊ ስብሰባዎች ላይ ኢትዮጵያን በመወከል፣ አንዳንዴም በልኡካን ቡድን አባልነት ታድሟል። እ.ኤ.አ በ1990/91 መንግሥት ከሻዕቢያ ጋር የሰላም ውይይት በመጀመሪያ በአትላንታ ጆርጂያ በካርተር ማዕከል፣ ቀጥሎ ኹለተኛና ሦስተኛ ዙሮች በዋሽንግተንና በኬንያ ናይሮቢ በተካኼደበት ጊዜ የልኡካኑ ቃል አቀባይ ብቻ ሳይሆን የጋዜጠኞችን ቡድን በመምራት ተሳትፏል።
ከአለቆቹ ጋር በመነጋገር በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ የCNN ሥርጭት አገልግሎት እንዲጀመር ያደረገውም እርሱ ነው። አዲስ ዘመን ዋና አዘጋጅ በነበረበት ጊዜ ታደሰ ውቤ ያዘጋጀው በነበረው የፍትሕ ዓምድ አማካኝነት በጊዜው አብዮታዊ ዘመቻ ኮሚቴ (አዘኮ) በሚባል ‘‘ተቋም’’ በየክፍለ ሀገሩ የታሰሩ ንጹሐን ዜጎች እንዲፈቱ አስችሏል።
በወቅቱ የግብፅ ፕሬዚዳንት አንዋር ሳዳት ወደ ሥልጣን የመጡበትን 10ኛ ዓመት በዓል ላይ ለመታደም ከሌሎች ባልደረቦች ጋር ወደ ካይሮ ያቀና ሲኾን፥ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት መምሪያ ሐላፊ በነበረበት ጊዜም የአፍሪካ ዜና አገልግሎት PANA በአዲስ አበባ ሲቋቋም፣ በኋላም በሴኔጋል ዳካር ጽሕፈት ቤቱ በተደረገ ስብሰባ ተካፍሏል።
የመጀመሪያው ‘‘Council of minister of information of non-aligned countries (COMINACI)’’ ጉባኤ በህንድ ኒውዴልሂ ሲካኼድ ኢትዮጵያን በመወከል በስብሰባው ላይ ተካፍሏል። ይኸው ጉባኤ በኢንዶኒዥያ ጃካርታ ሲካኼድ የልኡካን ቡድኑ አባል በመሆን ታድሟል።
ከዚህ ባሻገር የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ወደ ቀለም በተሸጋገረበት ወቅት፥ ሕዝቡ በየቤቱ ባለቀለም ሥርጭቱን የሚመለከትበት ቴሌቪዥን ኢትዮጵያ አልነበራትም። እናም በመንግሥት አስቸኳይ ትእዛዝ ርዳታ ለመጠየቅ በዶ/ር ፈለቀ ገድለ ጊዮርጊስ በተመራው የልኡካ ቡድን አባል በመሆን ወደ ጃፓን ቶክዮ በመሄድ ከማሩቤኒ ኩባንያ በመቶዎች የሚቆጠሩ ባለቀለም ቴሌቪዥኖች በርዳታ አግኝተው ተመልሰዋል።
ከዚህ በተጨማሪ ከሱዳን ዜና አገልግሎት (SUNA)፣ ከጀርመን ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክና ከሌሎች አገሮች የዜና አገልግሎት ተቋሞች ጋር የኹለትዮሽ ስምምነት ተፈራርሟል።
መርዕድ ካገኛቸው ሽልማቶች መካከል ኢትዮጵያን ሄራልድ በነበረበት ጊዜ በአዲስ አበባ ስታዲየም በተካኼደው መርሐ ግብር ‘‘የዓመቱ ምርጥ ጋዜጠኛ’’ በመባል የምስክር ወረቀት አግኝቷል። በአዲስ ዘመን ዋና አዘጋጅ ሳለም ዋና መሥሪያ ቤቱ ቬንዙዌላ ካራካስ ከሚገኝ ‘‘ኢንተርናሽናል ጎልድ ሜርኩሪ’’ ከተባለ ተቋም ተሸልሟል።
መርዕድ ወደ ስደት
መርዕድ በቀለ በግንቦት ወር 1983 ዓ.ም. ሕወሐት አዲስ አበባ ሊገባ አንድ ቀን ሲቀረው ነበር፥ በድሬዳዋ አድርጎ ዲክል በምትባል አነስተኛ የጅቡቲ የጠረፍ ከተማ የደረሰው። የጅቡቲ የደኅንነት ሰዎች እርሱንና ከርሱ ጋር የነበሩትን ሌሎች ሦስት ኢትዮጵያውያን አሰሯቸው። ዲክል ከአንድ ዓመት ከአራት ወራት የስደት ኑሮ በኋላ እ.ኤ.አ በ1992 ወደ አሜሪካ በማቅናት ከባለቤቱ እና ከአዳጊ ልጆቹ ጋር ተገናኝቶ ኹለተኛውን የስደት ኑሮ ምዕራፍ “ሀ” ብሎ ጀመረ።
በ1996 እኤአ በአትላንታ በተካኼደው 26ኛ የኦሎምፒክ ውድድር ወቅት የኢትዮጵያ መንግሥት መርዕድ በቀለ የኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ቡድን ባልደረባ (envoy) እንዲሆን አልስማማም በማለቱ፥ የዓለም አቀፉ አዘጋጅ ኮሚቴ የኡጋንዳ ኦሎምፒክ ቡድን ባልደረባ እንዲሆን ወሰነ። በዚኽ ሁኔታ መርዕድ በሙሉ የኦሎምፒክ ውድድር ላይ ከመታደሙ ባሻገር፥ በወቅቱ ኹለት የኡጋንዳ ቦክሰኞች ውድድራቸውን በማካኼድ ላይ እንዳሉ በወንጀል በመታሰራቸው በግሉ ዋስ በመሆን ከእስር እንዲፈቱና ውድድራቸውን እንዲጨርሱ ረድቷቸዋል።
እኤአ 2019/20 የዓለማችን ከፍተኛ ሥጋት የነበረው የኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ 19) ወረርሽኝ በአገራችንም በተከሠተ ጊዜ ሥርጭቱን ለመግታትና ወገኖችን ለመርዳት በኢትዮጵያ መንግሥት የቀረበውን የድጋፍ ጥሪ ተቀብሎ በአበረከተው በጎ አስተዋፅኦ ከአምባሳደር ፍጹም አረጋ የምስጋና የምስክር ወረቀት ተሰጥቶታል፡፡
መርዕድ በጆርጂያ
መርዕድ በጆርጅያ ‘‘Department of juvenile justice’’ በሚባል መንግሥታዊ መሥሪያ ቤት ውስጥ በአይ. ቲ. ክፍል ለ13 ዓመታት አገልግሏል። ከዚህ በኋላ በአትላንታ ትልቁ የታክሲ ኩባንያ ‘የሎው ካብ’ yellow cub የአትላንታው ቅርንጫፍ ምክትል ፕሬዚዳንት ሆኖ ጡረታ እስከወጣበት እስከ 2020 ዓ.ም. በርካታ ኢትዮጵያውያንን የዩጋንዳ፣ የኬንያ፣ የሱዳንና የበርታ አረብ ሀገር ዜጎችን አገልግሏል።
ከዚህ ሌላ በአትላንታ መጀመሪያ አካባቢ ወርሃዊ ጋዜጣ ማሳተም ጀምሮ ነበር። ሆኖም ከጥቂት ዕትሞች በኋላ በተለያየ ምክንያት ሊቀጥል ባለመቻሉ ኅትመቱ ቆሟል።
እ.ኤ.አ በ1994 የማኅደረ አንድነት የሲቪክ ማኅበር በተቋቋመ በዓመቱ የሬዲዮ ፕሮግራም ሲከፈት ከሌሎች ባልደረቦቹ ጋር በመሆን የሬዲዮ ፕሮግራሙን ይዘት፣ ፖሊሲና የመሳሰሉትን በመጻፍ ከፍተኛ አስተዋፅኦ አበርክቷል።
መርዕድ የኢትዮጵያና የአሜሪካ ግንኙነት ይበልጥ እንዲጠናከርና የአሜሪካ ምክር ቤት ኢትዮጵያን የሚጎዳ ሕግ እንዳያወጣ የሚታገለው፥ በኢትዮጵያውያን የተቋቋመው የመጀመሪያው የlobyalot ድርጅት ‘‘American Ethiopian Public Affair Committee’’ የአትላንታ ቅርንጫፍ ሊቀመንበር ሆኖ በማገልገል ላይ ነው።
አቶ መርዕድ በቀለ ለ49 ዓመታት የትዳር አጋሩ ከሆነችው ከወይዘሮ ኤፍራት እንደሻው፤ኤፍራት ቤሉል መርዕድ እና ዮናታን መርዕድ የተባሉትን ልጆቻቸውን አፍርተዋል፡፡ ሶፍያ ካሊዬሮ ደግሞ የልጅ ልጃቸው ናት፡፡ ለቤተሰቡ መፅናናት ይሁን።
. በደርግ ጊዜ የማስታወቂያ ምክትል ሚኒስትር ነበር
ከዕዝራ እጅጉ (ተወዳጅ ሚድያ)
#ታሪክ በኢትዮጵያን ሄራልድ፣በየዛሬይቱ ኢትዮጵያ ጋዜጦች፣እንዲሁም በኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት በመምሪያ ኃላፊነት ያገለገለው አቶ መርዕድ በቀለ ትናንት ህዳር 4 2018 በአትላንታ ህይወቱ ማለፉ ተሰምቷል።
የደርግ ዘመን ማብቂያ ላይ የማስታወቂያ ምክትል ሚኒስትር የነበረው የሚድያ ሰው አቶ መርዕድ በሥነ ፅሁፍ ችሎታው የተመሠከረለት ነበር። የሕይወት ታሪኩ የአማርኛ ኢንሳይክሎፒዲያ "መዝገበ አእምሮ ቅፅ ሁለት ላይ የሰፈረለት አቶ መርዕድ በቀለ በ2016 በተደረገው የክብር ሽልማት የህይወት ዘመን ተሸላሚዎች ከእጩዎቹ አንዱ ነበር።
አቶ መርዕድ ተወዳጅ ሚድያ የሚያከናውናቸውን የስነዳ ሥራዎች የሚደግፍ ፣ የሚያበረታታ የቅርብ ሰው ሲሆን በህልፈቱም የተሰማንን ሀዘን እንገልጻለን። የካቲት 26 2018 ሲመጣ 80 ዓመቱን ይይዝ የነበረው አቶ መርዕድ ከሰዎች ጋር በቀላሉ የሚግባባ እና የፅሑፍ ሥራንም በጥንቃቄ የሚያከናውን ነበር። እኛም የህይወት ታሪኩን እንደሚከተለው እናቀርባለን።
ትውልድ እና ልጅነት
መርዕድ በቀለ በ1938 ዓ.ም. የካቲት 26 ቀን አዲስ አበባ ቀጨኔ መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን አካባቢ ተወለደ። አባቱ አቶ በቀለ ወ/ኪዳን የአብነት ትምህርት ቤት ገብቶ የቤተ ክርስቲያን ትምህርት እንዲማር ፍላጎቱ ቢኖራቸውም፣ እናቱ ወ/ሮ ጽጌ ወርቅ ተክለ ጻዲቅ ግን ልጃቸው ከአጠገባቸው እንዳይርቅ በማሰብ በቤት ውስጥ መምህር ቀጥረው ፊደል ከቆጠረ በኋላ በአካባቢው በነበረው የየኔታ ትምህርት ቤት ገባ።
ትምህርት
በኋላም በአምኃ ደስታ የአንደኛ፣ በዳግማዊ ምኒልክ ትምህርት ቤት ደግሞ የኹለተኛ ደረጃ ትምህርቱን አጠናቀቀ። አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ገብቶ በውጭ ቋንቋዎች እና ሥነጽሑፍ በእንግሊዘኛ ቋንቋ በ1965 ዓ.ም. ተመረቀ።
ወደ ሥራ ዓለም
በዚያው ዓመት ነበር በቀድሞው ልዩ ካቢኔ ቢሮ በታላቁ ቤተመንግሥት ውስጥ የተቀጠረው። ልዩ ካቢኔ በነበረበት ወቅትም ዋና ሥራው ከተለያዩ የዓለም ዜና ምንጮች (Reuters, AFP, BBC… ወዘተ) ከሚሠራጩ ዜናዎች ውስጥ የተመረጡትን እየተረጎመ በአለቃው በኩል ለንጉሡ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ማቅረብ ነበር። ሆኖም በዚህ ሥራ ከሦስት ሳምንት በላይ አልዘለለም።
በወቅቱ የማስታወቂያ ሚኒስቴር ለኢትዮጵያን ሄራልድ እንግሊዘኛ ጋዜጣ የሪፖርተር ቅጥር ያወጣውን ፈተና አልፎ፥ የማታ ኤዲተር ሆኖ ሥራ ጀመረ። ብዙም ሳይቆይ ወደ ቀን ተዘዋወረ።
የህትመት ሚድያ
መርዕድ በ1967 ዓ.ም. ባገኘው የትምህርት ዕድል ወደ ሞስኮ አቅንቶ ነበር። በዚያም ለአንድ ዓመት ስለ ሶሻሊዝም ፅንሰ ሐሳብ ካጠና በኋላ ወደ አገሩ ተመልሶ በዚያው በኢትዮጵያን ሄራልድ በአዘጋጅነት ለተወሰኑ ዓመታት አገልግሏል። ቀጥሎም ወደ “የዛሬይቱ ኢትዮጵያ” ጋዜጣ በዋና አዘጋጅነት ዕድገት አግኝቶ እንዲሠራ ተደረገ። ብዙም ሳይቆይ ወደ አዲስ ዘመን ዕለታዊ ጋዜጣ በዕድገት ተዛውሮ በምክትል ዋና አዘጅነት ለኹለት ዓመታት ከሠራ በኋላ ዋና አዘጋጅ ሆኖ እንዲሠራ ተመደበ።
ከኢዜአ እስከ ምክትል ሚኒስትር
በሥራው ባሕርይ የተነሣ መርዕድ በተደጋጋሚ ‘‘ለጥያቄ ትፈለጋለህ’’ እየተባለ ወደ ደርግ ጽሕፈት ቤት ይጠራ ነበር። እንደ እኤአ 1975/76 ሁለት የደኅንነት ሰዎች ከመሥሪያ ቤቱ መጥተው ወደ ማዕከላዊ እስር ቤት ወሰዱት። ሁኔታው ነገሩ ለሕይወቱ እንደሚያሰጋው በመገንዘብ ከቦታው እንዲዛወር አለቃው የነበረውን ደራሲ በዓሉ ግርማን ደጋግሞ ይጠይቅ፣ ይወተውትም ጀመር። ውትወታው ተቀባይነት አግኝቶ በዕድገት የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ሐላፊ ሆኖ ተዛወረ፡፡ እዚያ ለአንድ ዓመት እንደቆየ፥ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት መምሪያ ሐላፊ ሆኖ እንዲሠራ ተመደበ። ለኹለት ዓመታት ካገለገለ በኋላ፥ ከሀገር እስከወጣበት ጊዜ ድረስ የማስታወቂያ ምክትል ሚኒስትር ሆኖ አገልግሏል።
አበርክቶ
መርዕድ በሥራ ላይ በነበረበት ጊዜ በተለያዩ ዓለም አቀፍና አህጉራዊ ስብሰባዎች ላይ ኢትዮጵያን በመወከል፣ አንዳንዴም በልኡካን ቡድን አባልነት ታድሟል። እ.ኤ.አ በ1990/91 መንግሥት ከሻዕቢያ ጋር የሰላም ውይይት በመጀመሪያ በአትላንታ ጆርጂያ በካርተር ማዕከል፣ ቀጥሎ ኹለተኛና ሦስተኛ ዙሮች በዋሽንግተንና በኬንያ ናይሮቢ በተካኼደበት ጊዜ የልኡካኑ ቃል አቀባይ ብቻ ሳይሆን የጋዜጠኞችን ቡድን በመምራት ተሳትፏል።
ከአለቆቹ ጋር በመነጋገር በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ የCNN ሥርጭት አገልግሎት እንዲጀመር ያደረገውም እርሱ ነው። አዲስ ዘመን ዋና አዘጋጅ በነበረበት ጊዜ ታደሰ ውቤ ያዘጋጀው በነበረው የፍትሕ ዓምድ አማካኝነት በጊዜው አብዮታዊ ዘመቻ ኮሚቴ (አዘኮ) በሚባል ‘‘ተቋም’’ በየክፍለ ሀገሩ የታሰሩ ንጹሐን ዜጎች እንዲፈቱ አስችሏል።
በወቅቱ የግብፅ ፕሬዚዳንት አንዋር ሳዳት ወደ ሥልጣን የመጡበትን 10ኛ ዓመት በዓል ላይ ለመታደም ከሌሎች ባልደረቦች ጋር ወደ ካይሮ ያቀና ሲኾን፥ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት መምሪያ ሐላፊ በነበረበት ጊዜም የአፍሪካ ዜና አገልግሎት PANA በአዲስ አበባ ሲቋቋም፣ በኋላም በሴኔጋል ዳካር ጽሕፈት ቤቱ በተደረገ ስብሰባ ተካፍሏል።
የመጀመሪያው ‘‘Council of minister of information of non-aligned countries (COMINACI)’’ ጉባኤ በህንድ ኒውዴልሂ ሲካኼድ ኢትዮጵያን በመወከል በስብሰባው ላይ ተካፍሏል። ይኸው ጉባኤ በኢንዶኒዥያ ጃካርታ ሲካኼድ የልኡካን ቡድኑ አባል በመሆን ታድሟል።
ከዚህ ባሻገር የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ወደ ቀለም በተሸጋገረበት ወቅት፥ ሕዝቡ በየቤቱ ባለቀለም ሥርጭቱን የሚመለከትበት ቴሌቪዥን ኢትዮጵያ አልነበራትም። እናም በመንግሥት አስቸኳይ ትእዛዝ ርዳታ ለመጠየቅ በዶ/ር ፈለቀ ገድለ ጊዮርጊስ በተመራው የልኡካ ቡድን አባል በመሆን ወደ ጃፓን ቶክዮ በመሄድ ከማሩቤኒ ኩባንያ በመቶዎች የሚቆጠሩ ባለቀለም ቴሌቪዥኖች በርዳታ አግኝተው ተመልሰዋል።
ከዚህ በተጨማሪ ከሱዳን ዜና አገልግሎት (SUNA)፣ ከጀርመን ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክና ከሌሎች አገሮች የዜና አገልግሎት ተቋሞች ጋር የኹለትዮሽ ስምምነት ተፈራርሟል።
መርዕድ ካገኛቸው ሽልማቶች መካከል ኢትዮጵያን ሄራልድ በነበረበት ጊዜ በአዲስ አበባ ስታዲየም በተካኼደው መርሐ ግብር ‘‘የዓመቱ ምርጥ ጋዜጠኛ’’ በመባል የምስክር ወረቀት አግኝቷል። በአዲስ ዘመን ዋና አዘጋጅ ሳለም ዋና መሥሪያ ቤቱ ቬንዙዌላ ካራካስ ከሚገኝ ‘‘ኢንተርናሽናል ጎልድ ሜርኩሪ’’ ከተባለ ተቋም ተሸልሟል።
መርዕድ ወደ ስደት
መርዕድ በቀለ በግንቦት ወር 1983 ዓ.ም. ሕወሐት አዲስ አበባ ሊገባ አንድ ቀን ሲቀረው ነበር፥ በድሬዳዋ አድርጎ ዲክል በምትባል አነስተኛ የጅቡቲ የጠረፍ ከተማ የደረሰው። የጅቡቲ የደኅንነት ሰዎች እርሱንና ከርሱ ጋር የነበሩትን ሌሎች ሦስት ኢትዮጵያውያን አሰሯቸው። ዲክል ከአንድ ዓመት ከአራት ወራት የስደት ኑሮ በኋላ እ.ኤ.አ በ1992 ወደ አሜሪካ በማቅናት ከባለቤቱ እና ከአዳጊ ልጆቹ ጋር ተገናኝቶ ኹለተኛውን የስደት ኑሮ ምዕራፍ “ሀ” ብሎ ጀመረ።
በ1996 እኤአ በአትላንታ በተካኼደው 26ኛ የኦሎምፒክ ውድድር ወቅት የኢትዮጵያ መንግሥት መርዕድ በቀለ የኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ቡድን ባልደረባ (envoy) እንዲሆን አልስማማም በማለቱ፥ የዓለም አቀፉ አዘጋጅ ኮሚቴ የኡጋንዳ ኦሎምፒክ ቡድን ባልደረባ እንዲሆን ወሰነ። በዚኽ ሁኔታ መርዕድ በሙሉ የኦሎምፒክ ውድድር ላይ ከመታደሙ ባሻገር፥ በወቅቱ ኹለት የኡጋንዳ ቦክሰኞች ውድድራቸውን በማካኼድ ላይ እንዳሉ በወንጀል በመታሰራቸው በግሉ ዋስ በመሆን ከእስር እንዲፈቱና ውድድራቸውን እንዲጨርሱ ረድቷቸዋል።
እኤአ 2019/20 የዓለማችን ከፍተኛ ሥጋት የነበረው የኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ 19) ወረርሽኝ በአገራችንም በተከሠተ ጊዜ ሥርጭቱን ለመግታትና ወገኖችን ለመርዳት በኢትዮጵያ መንግሥት የቀረበውን የድጋፍ ጥሪ ተቀብሎ በአበረከተው በጎ አስተዋፅኦ ከአምባሳደር ፍጹም አረጋ የምስጋና የምስክር ወረቀት ተሰጥቶታል፡፡
መርዕድ በጆርጂያ
መርዕድ በጆርጅያ ‘‘Department of juvenile justice’’ በሚባል መንግሥታዊ መሥሪያ ቤት ውስጥ በአይ. ቲ. ክፍል ለ13 ዓመታት አገልግሏል። ከዚህ በኋላ በአትላንታ ትልቁ የታክሲ ኩባንያ ‘የሎው ካብ’ yellow cub የአትላንታው ቅርንጫፍ ምክትል ፕሬዚዳንት ሆኖ ጡረታ እስከወጣበት እስከ 2020 ዓ.ም. በርካታ ኢትዮጵያውያንን የዩጋንዳ፣ የኬንያ፣ የሱዳንና የበርታ አረብ ሀገር ዜጎችን አገልግሏል።
ከዚህ ሌላ በአትላንታ መጀመሪያ አካባቢ ወርሃዊ ጋዜጣ ማሳተም ጀምሮ ነበር። ሆኖም ከጥቂት ዕትሞች በኋላ በተለያየ ምክንያት ሊቀጥል ባለመቻሉ ኅትመቱ ቆሟል።
እ.ኤ.አ በ1994 የማኅደረ አንድነት የሲቪክ ማኅበር በተቋቋመ በዓመቱ የሬዲዮ ፕሮግራም ሲከፈት ከሌሎች ባልደረቦቹ ጋር በመሆን የሬዲዮ ፕሮግራሙን ይዘት፣ ፖሊሲና የመሳሰሉትን በመጻፍ ከፍተኛ አስተዋፅኦ አበርክቷል።
መርዕድ የኢትዮጵያና የአሜሪካ ግንኙነት ይበልጥ እንዲጠናከርና የአሜሪካ ምክር ቤት ኢትዮጵያን የሚጎዳ ሕግ እንዳያወጣ የሚታገለው፥ በኢትዮጵያውያን የተቋቋመው የመጀመሪያው የlobyalot ድርጅት ‘‘American Ethiopian Public Affair Committee’’ የአትላንታ ቅርንጫፍ ሊቀመንበር ሆኖ በማገልገል ላይ ነው።
አቶ መርዕድ በቀለ ለ49 ዓመታት የትዳር አጋሩ ከሆነችው ከወይዘሮ ኤፍራት እንደሻው፤ኤፍራት ቤሉል መርዕድ እና ዮናታን መርዕድ የተባሉትን ልጆቻቸውን አፍርተዋል፡፡ ሶፍያ ካሊዬሮ ደግሞ የልጅ ልጃቸው ናት፡፡ ለቤተሰቡ መፅናናት ይሁን።
9 months ago
ሽህ አርሶ አደሮቸን የፋብሪካ ባለቤት ያደረገው አድማስ ዩኒዬን
#ethiopia | አድማስ ሁለ/የገበ/የኀ/ሥ/ማኀበራት ዩኒዬን ኃ.የተ ዩኒዬን በ1996ዓ.ም በውስን በጀት እና በጥቂት አባል መሰረታዊ ህብረት ስራ ማህበራት ይሁንታ የተደራጅ ነው።
አሁን ላይ በአማራ ክልል ብሎም በሀገር አቀፍ ደረጃ በካፒታል አቅማቸው ጠንካራ ከሆኑ የህብረት ስራ በቀዳሚነት ከሚጠቀሱት ዩኒየኖች መካከል አንዱ መሆኑን የዩኒየኑ ዋና ስራአስኪያጅ መሠረት ወርቄ ይናገራሉ።
በህብረት ስራ ማህበራት መደራጀት ጉልበት፣ እውቀትንና ገንዘብን አንድ ላይ በማሰባሰብ ሁኔታዎችን በመለወጥ የኢኮኖሚ ሀይል መፈጠር እንደሚቻል አድማስ ዩኒዬን ማሳያ ነው።
"ከአንድ ብርቱ ሁለት መድኃኒቱ" እንደሚባለው መደራጀት ሀይል ሆኖ እነሆ አድምስ እንደአድማስነቱ ለተቋቋመለት አላማ ከጊዜ ወደ ጊዜ ተጨባጭ ውጤቶችን እያስመዘገበ ይገኛል።
ዩኒዬን ከመነሻው ሁሉን አብቃይ በሆነው በአዊ ብሄ/አስ የስራ አድማሱን መሰረት በማድረግ የተቋቋመ ነው።
በዋናነት ለአባል አ/አደሮች የምርት ማሳደጊያ ግብዓትና ቴክኖሎጂ ማቅረብ አባላት ያመረቱትን ምርት ከአባል አ/አደሮች በተመጣጣኝ ዋጋ በመግዛት ገበያ ላይ ተወዳዳሪ ሆኖ በመሸጥ የትርፍ ተጠቃሚ ማድረግ፣ የትምህርትና ስልጠና አገልግሎት መስጠት፣የትራንስፖርትና የመጋዝን አገልግሎት መስጠትን ዋና አላማ አድርጐ ተመሰረተ።
ዩኒዬኑ የብሄረሰብ አስተዳደሩ አርሶ አደሮች ምርትና ምርታማነትን የሚጨምሩ የግብርና ግብዓቶች፣ትክኖሎጅዎች ማለትም 6 ትራክተሮችን እና በርከት ያሉ ኮምባይነሮች በማቅረብ ለአርሶ አደሩ የሙሉ ፓኬጅ ሜካናይዜሽን አገልግሎት በመስጠት ከፍተኛ አስተዋፅኦ እያበረከተ ይገኛል።
አርሶ አደር አባላት ያመረቱት ሰሊጥና አኩሪ አተር ምርት በዩኒየኑ በኩል ተሰብስቦ ወደ ውጭ በመላክ የውጭ ምንዛሬ በማስገኘት አርሶአደሩን ተጠቃሚ እያደረገ ያለ ግዙፍ የህዝብ ተቋምም ነው።
ዩኒዬኑ የቀረጢት፣የእንስሳት መኖ ማቀነባበሪያ ፣የምንጣፍ ፋብሪካዎችን ገምብቶ ምርት በማምረት ለሀገር ውስጥ ገበያ እያቀረበ ይገኛል።የምድር ሚዛን አገልግሎትም ይሰጣል።አድማስ በብሄረሰብ አስተዳደሩ ውስጥ በርካታ ዘመናዊ የእህል ማከማቻ መጋዘኖችም አሉት።
በአሁኑ ስዓት በውጭ አገር ኢንፖርት ኤክስፖርት ምርት ግብይት በግብርናና ሜካናይዜሽን፣በአግሮ ፕሮሰሲንግ፣በማኒፋክቸሪንግ ትላልቅ ኢንዱስትሪዎችን በመክፈት አገልግሎት በመስጠት ላይ ሲሆን፦ በዚህም ከ179ሽህ በላይ አባል አርሶአደሮችን የፋብሪካ ባለቤት በማድረግ ተጠቃሚ እያደረገ ይገኛል።
ከሰሞኑ አድማስ ሁለገብ የገበሬዎች የህብረት ስራ ማህበራት ዩኒዬን ግብርናን ለማዘመን ያስገባቸው አዳዲስ ለአባል አሬሶአደሮች የምርትና የግብዓት መጓጓዣነት የሚያገለግሉ በቁጥር 13 ካሶኒ ተሽከርካሪዎችና 60 የሚሆኑ የበቆሎ መፈልፈያ ማሽኖች ባካሄደው መደበኛ ጉባኤው ይፋ አድርጓል።
ያኔ ሲመሰረት በ800ሽህ ብር ባልበለጠ መነሻ ካፒታል ይዞ ስራ የጀመረው አድማስ አሁን ላይ ካፒታሉን 253 ሚሊዮን 194 ሽህ 107.68 ማድረስ ችሏል።
ዩኒዬኑ የአሠራር አድማሱን በማስፋት ራዕዩን ‹‹በምስራቅ አፍሪካ ጠንካራ ተወዳዳሪ የኀብረት ስራ ማኀበራት ዩኒዬን ሆኖ ማየት ራዕይ ሰንቆ እየተቀሳቀሰ ይገኛል።
#ethiopia | አድማስ ሁለ/የገበ/የኀ/ሥ/ማኀበራት ዩኒዬን ኃ.የተ ዩኒዬን በ1996ዓ.ም በውስን በጀት እና በጥቂት አባል መሰረታዊ ህብረት ስራ ማህበራት ይሁንታ የተደራጅ ነው።
አሁን ላይ በአማራ ክልል ብሎም በሀገር አቀፍ ደረጃ በካፒታል አቅማቸው ጠንካራ ከሆኑ የህብረት ስራ በቀዳሚነት ከሚጠቀሱት ዩኒየኖች መካከል አንዱ መሆኑን የዩኒየኑ ዋና ስራአስኪያጅ መሠረት ወርቄ ይናገራሉ።
በህብረት ስራ ማህበራት መደራጀት ጉልበት፣ እውቀትንና ገንዘብን አንድ ላይ በማሰባሰብ ሁኔታዎችን በመለወጥ የኢኮኖሚ ሀይል መፈጠር እንደሚቻል አድማስ ዩኒዬን ማሳያ ነው።
"ከአንድ ብርቱ ሁለት መድኃኒቱ" እንደሚባለው መደራጀት ሀይል ሆኖ እነሆ አድምስ እንደአድማስነቱ ለተቋቋመለት አላማ ከጊዜ ወደ ጊዜ ተጨባጭ ውጤቶችን እያስመዘገበ ይገኛል።
ዩኒዬን ከመነሻው ሁሉን አብቃይ በሆነው በአዊ ብሄ/አስ የስራ አድማሱን መሰረት በማድረግ የተቋቋመ ነው።
በዋናነት ለአባል አ/አደሮች የምርት ማሳደጊያ ግብዓትና ቴክኖሎጂ ማቅረብ አባላት ያመረቱትን ምርት ከአባል አ/አደሮች በተመጣጣኝ ዋጋ በመግዛት ገበያ ላይ ተወዳዳሪ ሆኖ በመሸጥ የትርፍ ተጠቃሚ ማድረግ፣ የትምህርትና ስልጠና አገልግሎት መስጠት፣የትራንስፖርትና የመጋዝን አገልግሎት መስጠትን ዋና አላማ አድርጐ ተመሰረተ።
ዩኒዬኑ የብሄረሰብ አስተዳደሩ አርሶ አደሮች ምርትና ምርታማነትን የሚጨምሩ የግብርና ግብዓቶች፣ትክኖሎጅዎች ማለትም 6 ትራክተሮችን እና በርከት ያሉ ኮምባይነሮች በማቅረብ ለአርሶ አደሩ የሙሉ ፓኬጅ ሜካናይዜሽን አገልግሎት በመስጠት ከፍተኛ አስተዋፅኦ እያበረከተ ይገኛል።
አርሶ አደር አባላት ያመረቱት ሰሊጥና አኩሪ አተር ምርት በዩኒየኑ በኩል ተሰብስቦ ወደ ውጭ በመላክ የውጭ ምንዛሬ በማስገኘት አርሶአደሩን ተጠቃሚ እያደረገ ያለ ግዙፍ የህዝብ ተቋምም ነው።
ዩኒዬኑ የቀረጢት፣የእንስሳት መኖ ማቀነባበሪያ ፣የምንጣፍ ፋብሪካዎችን ገምብቶ ምርት በማምረት ለሀገር ውስጥ ገበያ እያቀረበ ይገኛል።የምድር ሚዛን አገልግሎትም ይሰጣል።አድማስ በብሄረሰብ አስተዳደሩ ውስጥ በርካታ ዘመናዊ የእህል ማከማቻ መጋዘኖችም አሉት።
በአሁኑ ስዓት በውጭ አገር ኢንፖርት ኤክስፖርት ምርት ግብይት በግብርናና ሜካናይዜሽን፣በአግሮ ፕሮሰሲንግ፣በማኒፋክቸሪንግ ትላልቅ ኢንዱስትሪዎችን በመክፈት አገልግሎት በመስጠት ላይ ሲሆን፦ በዚህም ከ179ሽህ በላይ አባል አርሶአደሮችን የፋብሪካ ባለቤት በማድረግ ተጠቃሚ እያደረገ ይገኛል።
ከሰሞኑ አድማስ ሁለገብ የገበሬዎች የህብረት ስራ ማህበራት ዩኒዬን ግብርናን ለማዘመን ያስገባቸው አዳዲስ ለአባል አሬሶአደሮች የምርትና የግብዓት መጓጓዣነት የሚያገለግሉ በቁጥር 13 ካሶኒ ተሽከርካሪዎችና 60 የሚሆኑ የበቆሎ መፈልፈያ ማሽኖች ባካሄደው መደበኛ ጉባኤው ይፋ አድርጓል።
ያኔ ሲመሰረት በ800ሽህ ብር ባልበለጠ መነሻ ካፒታል ይዞ ስራ የጀመረው አድማስ አሁን ላይ ካፒታሉን 253 ሚሊዮን 194 ሽህ 107.68 ማድረስ ችሏል።
ዩኒዬኑ የአሠራር አድማሱን በማስፋት ራዕዩን ‹‹በምስራቅ አፍሪካ ጠንካራ ተወዳዳሪ የኀብረት ስራ ማኀበራት ዩኒዬን ሆኖ ማየት ራዕይ ሰንቆ እየተቀሳቀሰ ይገኛል።
10 months ago
የሀርቫርድ ምሩቁ የቀድሞ የብሔራዊ ባንክ ገዢ ልጅ የወንድወሰን መንገሻ በ97 ዓመታቸው አረፉ
ዕዝራ እጅጉ-(ተወዳጅ ሚድያ)
ታሕሣስ 24 ቀን 1920 ዓም - ጥቅምት 2 ቀን 2018 ዓ.ም
ቀብራቸው ሐሙስ ጥቅምት 13 በለንደን ይፈፀማል
#ethiopia | ተወዳጅ ሚድያ እና ኮምዩኒኬሽን ፣ መዝገበ-አእምሮ ( የአማርኛ ኢንሳይክሎፒዲያ ) ፕሮጀክቱ ለአገር የሠሩ ሰዎችን ታሪክ እየሰነደ እንደሆነ ይታወቃል። ይህ ታሪክ በዲጂታል ሚድያዎች ፣በመፅሀፍ፣በድምፅ ትረካና በሌሎችም መንገዶች እየቀረበ እንደሆነ ይታወቃል። ባለፉት 4 ዓመት ከ 5 ወር ጊዜ ውስጥ የ423 ሰዎችን የሕይወትና የሥራ ታሪክ ለመሰነድ የቻልን ሲሆን 600 ገፅ ባላቸው ሁለት የተለያዩ መፅሐፎች ላይም ታሪኮቹ ዘመን ተሻጋሪ ሆነው እንዲቀመጡ አድርገናል።
ቅፅ 3 መዝገበ አእምሮ ከ20 በላይ ዘርፎች ይኖሩታል። እዚህ ዘርፍ ውስጥ የሚገኙ የአገር ባለውለታዎችን መሰነዳችን ይቀጥላል። የባንክ፣ የፋይናንስ እና የኢንሹራንስ በሚለው ዘርፍ ውስጥ ታሪካቸው የሚሰነደው ልጅ የወንድወሰን መንገሻ ሲሆኑ ታሪካቸውንም ዕዝራ እጅጉ ሰንዶታል።
የሐርቫርድ ዩኒቨርሲቲ የግራጅዌት ቢዝነስ ትምህርት ቤት የታላቅ አገልግሎት እና ለቀድሞ ተማሪዎች የሥራ ስኬት ተብሎ የተሰየመውን ሽልማት ለልጅ የወንድወሰን መንገሻ እ ኤ አ በ1996 ዓ.ም ሲሰጣቸው በመጀመሪያ የእርሳቸውን ማንነት መገለጫ ያደረገው “ሰብዓዊነትን የረዱ” በማለት እና በምስጋናው መዝጊያ ላይ ደግሞ “ለዓለም ደህንነት የታቻላቸውን አስተዋጽኦ ያበረከቱ” ሲል ዩኒቨርሲቲው አድናቆቱን በሚገባ ገልጿል።
የተከበሩ አባታቸው አባ መንገሻ ገነሜ (ቀደም ሲል ፊታውራሪ) የግርማዊ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዘመድ ነበሩ። እናታቸው ወይዘሮ ተዋበች ዛማኑኤል በወራሪው ፋሽስት በግፍ ታስረው በተወሰዱበት ኢጣልያ አገር ውስጥ ሕይወታቸው አልፏል። አክስታቸው ወ/ሮ ሉልአደይ ዛማኑኤል ልጅ የወንደሰንን እና ታናሽ እህቶቻቸውን ወ/ሪት ኮከቤ መንገሻን እና ወ/ሮ እግዚሐርያ መንገሻን እንደ ልጆቻቸው በፍቅር አሳድገዋቸዋል። ልጅ ከበደ ኃይሌ ታላቅ ወንድማቸው ነበሩ።
ልጅ የወንድወሰን የአንደኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በተፈሪ መኮንን እና በፕሪንቺፔ ዲ ፒያሞንቴ ትምህርት ቤቶች ከተማሩ በኋላ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን አቃቂ በሚገኘው የአድቬንቲስት ሚሲዮን እና አዲስ አበባ በሚገኘው ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ተምረው አጠናቅቀዋል። ቀጥሎም፣ በጊዜው የሎንዶን ዩኒቨርሲቲ አካል የነበረው ሳውዝሃምፕተን ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ ተቀብሏቸው በኢትዮጵያ መንግሥት የነፃ ትምህርት ዕድል ድጋፍ ተምረው እ ኤ አ በ1954 ዓ.ም በኢኮኖሚክስ እና አካውንቲንግ በከፍተኛ ማዕረግ ተመረቁ። ኮሌጅ የተማረ የመጀመሪያው የቤተሰቡ አባል እንደመሆናቸው መጠን ወደ እናት አገራቸው ሲመለሱ ሌሎችን ለመርዳት ይጓጉ ነበር። እውቀታቸውን እና ተሞክሯቸውን ለማስፋት ወደ አሜሪካ ሲጓዙ አስፈላጊው ገንዘብ ስላልነበራቸው ቦስተን ለመድረስ ወደካናዳ በሚጓዝ አንስተኛ የውቅያኖስ መስመር ላይ በአስተናጋጅነት በመሥራት ሀሳባቸውን አሳክተዋል። ከእዚያም እ ኤ አ በ1956 ዓ.ም ከሐርቫርድ ዩኒቨርሲቲ በኤም ቢ ኤ (MBA) ዲግሪ ተመረቁ።
ልጅ የወንድወሰን መንገሻ ፣ወደ ኢትዮጵያ ከመመለሳቸው በፊት ዶክተር አልበርት ሸቫይጸርን ለማግኘት ምዕራብ መካከለኛው አፍሪቃ ውስጥ ሩቅ ሥፍራ ወደሚገኝ ሆስፒታል ተጓዙ። ሆስፒታሉ ውስጥ ሁለት ሳምንታት ከቆዩ በኋላ ዶክተር ሸቫይጸርን የመሰለ ሌሎችን ለመርዳት የወሰኑ ሰውን መተዋወቅ ለወጣቱ ምሩቅ ታላቅ ክብር ነበር። በሆስፒታሉ ያጋጠማቸው ተሞክሮ በአገራቸው ሕዝብ ሕይወት ላይ ለውጥ ለማምጣት እራሳቸውም በቁርጠኝነት እንዲሰለፉ አድርጓቸዋል።
ወደ የሚወዷት አገራቸው ከተመለሱ በኋላ የመጀመሪያ ሥራ ምድባቸው በኢትዮጵያ አየር መንገድ የከፍተኛ ማኔጅመንት ኃላፊነት ነበር። ቀጥሎም በገንዘብ ሚንስቴር የዳይሬክተርነት ሹመት አገኙ። በዚሁ ሥራቸው ላይ እንዳሉም በወቅቱ በልዑል ራሥ መንገሻ ሥዩም በሚመራው የኢትዮዽያ የአየር መንገድ ቦርድ አባል በመሆን አየር መንገዱ በተለይ አፍሪቃ ውስጥ በተሳካ ሁኔታ የተለያዩ የብሪያ መስመሮችን እንዲዘረጋ የአባልነታቸውን አስተዋጽኦ አበርክተዎል። የመጀመሪያዎቹን ቦይንግ ጄት ኤሮፕላኖች ለመግዛት በተደረገው ወሳኝ ድርድር ውስጥ ቁልፍ ሚና ነበራቸው።
በ1960 የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ምክትል ገዥ ሆነው ተሾሙ። ይህንን የተከበረ ቦታ ለመያዝ የመጀመሪያው ኢትዮጵያዊ ነበሩ። የባንኩን ተቋም ለማዘመን ጠቃሚ ተነሳሽነቶችን በመምራት እና በማስተባበር ለአሥራ አራት ዓመታት በዚያ ሥራ ላይ ቆይተዋል። ከብዙ ትሩፋቶቻቸው አንዱ የብሔራዊ ባንክ ሠራተኞችን ለተጨማሪ ሥልጠና ወደ ውጭ አገር ለመላክ ያደረጉት ብርቱ ጥረት እና ስኬታማ ተነሳሽነት ነበር። ይህ በአርቆ አሳቢነት ላይ የተመሠረተ ጥረት ቁጥራቸው እየጨመረ ለመጣው ልዩ የባንክ ሥራ መደቦች በሙያው የሠለጠኑ ኢትዮጵያውያን እና ኢትዮጵያውያትን መመደብ አስችሏል።
ልጅ የወንድወሰን መንገሻ የኢትዮጵያ መንግሥትን ወክለው ከሌሎች ሀገሮች የገንዘብ ሚኒስትሮች ጋር በመተባበር በዓለም አቀፍ የባንክ ማኅበረሰብ ውስጥ ንቁ ተሳትፎ አድርገዋል። በተለይም ልጅ የወንድወሰን መንገሻ የአፍሪቃን ኤኮኖሚ ለማሳደግ እና ድህነትን ለመቀነስ የታለመውን የአፍሪቃ ልማት ባንክን (AfDB) በሚመሠረትበት ጊዜ ቁልፍ ሚና ተጫውተዋል። ኢትዮጵያ መሥራች ባለአክሲዮን እንደመሆኗ መጠን ባንኩን በማቋቋም ረገድ ግንባር ቀደም እና ስኬታማ መሪነት አሳይታለች። ብዙዎች ይህንን ስኬት የብሔራዊ ባንክ ገዥ የአቶ ምናሴ ለማ እና ምክትል ገዥ የልጅ የወንድወሰን መንገሻ አርቆ አስተዋይነት እና አመራር ውጤት ነው ብለው ይመለከቱታል። በዓለም አቀፍ ፋይናንስ ላይ በነበራቸው ዕውቀት እና ባለራዕይ አመራር በ1980 ዎቹ ዓመታት አፍሪቃ ልማት ባንክ ካፒታሉን ለማሳደግ ክልላዊ ያልሆኑ ሀገራትም
(non-regional countries) እንዲሳተፉ መንገድ ከፍተዋል። ይህም ዛሬ የባንኩ የስኬት ታሪክ ነው።
ትጉህ እና ድንቅ አትዮጵያዊው ልጅ የወንድወሰን መንገሻ በባልደረቦቻቸው እና በመንግስት ከፍተኛ ባለሥልጣናት ዘንድ ሰፊ ክብር ያሰጡዋቸው አዕምሯዊ ችሎታቸው፣ የሀገራቸውን እድገት ለማፋጠን ያሳዩት ቁርጠኝነት እና ከሌሎች ጋር ተስማምቶ የመሥራት ችሎታቸው። ግርማዊ ንጉሠ ነገሥት የልጅ የወንድወሰን መንገሻን የአመራር ችሎታቸውን እና ለፍትሃዊነት ያላቸውን ጥልቀት በመመዘን የቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ የሽልማት ድርጅት አምስት ባለአደራዎች ውስጥ አንዱ አድርገው ሾመዋቸዋል። በዚህም ኃላፊነት ከ10 ዓመታት በላይ አገልግለዋል።
ልጅ የወንድወሰን መንገሻ እ ኤ አ 1974 ዓም በሚያዝያ ወር ዋሽንግተን ዲሲ በተካሄደው የአይ ኤም ኤፍ (IMF) ስብሰባ በመሳተፍ ላይ እንዳሉ በኢትዮጵያ የነበረው ሁኔታ አደገኛ እየሆነ መጣ። ሁኔታው እርሳቸውንና ሌሎች በሺዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያንን ከሚወዷት ሀገራቸው የለያቸው እና ማለቂያ የሌለው የመሰለው አሳዛኝ የግዳጅ ግዞት ዘመን መጀመሪያ ነበር። ባለቤታቸው እና ሦስቱም ልጆቻቸው ከእርሳቸው ጋር ለመሆን ወደ አሜሪካ መጓዝ ቻሉ። ልጅ የወንድወሰን ወደ ኢትዮጵያ መመለስ ጥሩ አማራጭ እንዳልሆነ ከተረዱ በኋላ ቅድሚያ የሰጡት ቤተሰቡን የሚያስተዳድሩበት በተለይም ልጆቻቸውን ለማስተማር የሚያስችል ሥራ መፈለጉን ነበር።
በዓለም አቀፍ ፋይናንስ መስክ በነበራቸው ሰፊ ዕውቀት እና ችሎታ ለንደን በሚገኘው First Boston Corporation (ፈርስት ቦስተን ኮርፖሬሽን) ሥራ ለማግኘት በቁ። ቀጥሎም በታማኝነታቸው እና በልዩ ችሎታቸው ወደ ማኔጂንግ ዳይሬክተርነት (Managing Director)
ደረጃ ዕድገት አገኙ። በኩባንያው ውስጥ ለብዙ ዓመታት በጥሩ መሪነት ከአገለገሉ በኃላ Associated African Financial Services (አሶሽየትድ አፍሪካን ፋይናንሽያል ሰርቪስስ) የሚባል የአማካሪ ድርጅት አቌቁመው በተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት ጉልህ በሆኑ ፕሮጀክቶች ላይ ከአሥር አመታት በላይ ሠርተዋል።
ልጅ የወንድወሰን መንገሻ በቀሪው ሕይወታቸውም እንደሁልጊዜው ሌሎችን ለመርዳት፣ ሀገራቸው እና ሕዝቡ ላደረገላቸው ውለታ ለመመለስ ትኩረት በማድረጋቸው ብዙ የበጎ አድራጎት ቡድኖችን፣ ቤተክርስቲያናትን እና ግለ ሰቦችን ከመርዳት ተቆጥበው አያውቁም። ቤቱ ይቁጠረው እንደሚባለው ሰው የማያውቀው አምላክ ግን የሚያየው ብዙ ችግረኛችን ደግፈዋል። በተለይ ኅብረተሰቡን ለመርዳት ካቋቋሙዎቸው ቅርሶች አንዱ ለውድ አባታቸው መታሰቢያ እንዲሆን ባሕር ዳር ውስጥ የከፈቱት “አባ መንገሻ ገነሜ የሕዝብ ቤተ መጻሕፍት እና የመረጃ ማዕከል” ነው።
ወጣቶች ትምህርታቸውን በትጋት እንዲቀጥሉ እና በሙሉ አቅማቸው ዓላማቸውን ለማሳካት እንዲጥሩ ለማበረታታት እና ለመደገፍ በምንም ዓይነት ወደኃላ አዩሉም ነበር። በተለይም ለከፍተኛ ትምህርት እድሎችን ለማስፋት ከነበራቸው ጽኑ ፍላጎት በራሳቸው እና በባለቤታቸው ወይዘሮ ሕይወት ስም በሃርቫርድ ቢዝነስ ትምህርት ቤት የትምህርት ብቃት ላላቸው የአፍሪቃውያን ተማሪዎች ስኮላርሺፕ አቋቀቁመው ብዙ ተማሪዋች ሊጠቅሙ ችለዎል።
በፍቅር ወንድዬ ተብለው የሚጠሩትን ልጅ የወንድወሰን መንገሻን የማወቅ ዕድል ያገኙ ሁሉ ተንከባካቢነታቸውን፣ ትሁትነታቸውን እና ለጋሥነታቸውን ይመሰክራሉ። ዘመዶችን፣ ጓደኞችን እንዲሁም ሌሎች ሰዎች መርዳት እና ምክር በመለገስ ረገድ የተቻላቸውን ሁሉ አድርገዋል። እንዲሁም ታዳጊ እና ወጣት የሆኑት ዘመዶቻቸው እንደአባት እና አማካሪ ያዩዋቸው ነበር። የቤተሰብ አባላት ታማኝነታቸውን እና ጥበባዊ ምክራቸውን ከፍ አድርገው ይመለከቷቸው ነበር። በተለይም የቅርብ ዘመዶቻቸው ከሆኑት ከራሥ አንዳርጋቸው መሳይ እና ከልዕልት ተናኘወርቅ ኃይለ ሥላሴ ፍቅር እና አክብሮት ምንግዜም አልተላያቸውም።
ልጅ የወንድወሰን እ ኤ አ ጥቅምት 12 ቀን 2025 በለንደን በሚገኘው ቤታቸው በቤተሰብ ተከበው በሰላም በማረፍ ከዚህ አለም ተለይተዋል።
በነሐሴ 23 ቀን 1UG4 ዓም እኤአ በትዳር ካገቡዋቸው ከውድ ባለቤታቸው ከወ/ሮ ሕይወት ጋር በፍቅር፣ በመከባበር እና በተድላ የዕድሜ ባለፀጋ ሆነው ያሬድ፣ ያድዋ እና የአደይን አፍርተዋል። የሰባት የልጅ ልጆች አያት ለመሆን በቅተዋል - ካሌብ፣ ሶፊያ፣ ሉላዴይ (ሊሊ)፣ ጌሊላ፣ አሸር፣ ፀጋ እና ኢያሱ ። ቤተሰቡ መሪ አባት የነበሩትን በሞት በማጣታቸው በታላቅ ሀዘን ላይ ቢወድቁም አምላክ ረጅም ዕድሜ ስለሰጣቸው እና ቤተሰቡን ፍቅር በተሞላበት አርአያነት በመምራታቸው በምስጋና ተሞልተዋል።
እኚህ ትሁት የኢየሱስ ክርስቶስ አገልጋይ ፣ ቅዱስ ጳውሎስ በ1ኛ ቆሮንቶስ 13 ላይ እንዳስተማረው የፍቅር ምሳሌ ሆነው ኖረዋል።
“ፍቅር ታጋሽ ነው፣ ፍቅር ደግ ነው፣ ፍቅር አይመቀኝም፣ ፍቅር አይታበይም፣ ፍቅር አይኰራም፣ ፍቅር ስነስርዓተቢስ አይደለም፣ ፍቅር የራሱን ጥቅም ብቻ ፈላጊ አይደለም፣ ፍቅር አይበሳጭም፣ ፍቅር ቢበደልም እንኳ በደልን እንደበደል አይቆጥርም፣ ፍቅር እውነት በሆነ ነገር ይደሰታል እንጂ ክፋት በሆነ ነገር አይደሰትም፣ ፍቅር ሁሉን ችሎ ይታገሳል፣ ፍቅር በሁሉም ላይ ተስፋ የደርጋል፣ ፍቅር በሁሉም ነገር ይጸናል”
ቸሩ አምላክ ነፍሳቸውን የዘላለም እረፍት ይስጥልን።
ቤተሰቡ ጓደኞቻቸው እና ዘመዶቻቸው ለላኩት አጽናኝ መልእክቶች እና የሀዘን መግለጫዎች ሁሉ ልባዊ ምስጋናቸውን ያቀርባሉ።ልጅ የወንድወሰን መንገሻ
ታሕሣስ 24 ቀን 1U20 ዓም - ጥቅምት 2 ቀን 2018 ዓም
የሐርቫርድ ዩኒቨርሲቲ የግራጅዌት ቢዝነስ ትምህርት ቤት የታላቅ አገልግሎት እና ለቀድሞ ተማሪዎች የሥራ ስኬት ተብሎ የተሰየመውን ሽልማት ለልጅ የወንድወሰን መንገሻ እ ኤ አ በ1UUG ዓም ሲሰጣቸው በመጀመሪያ የሳቸውን ማንነት መገለጫ ያደረገው “ሰብዓዊነትን የረዱ” በማለት እና በምስጋናው መዝጊያ ላይ ደግሞ “ለዓለም ደህንነት የታቻላቸውን አስተዋጽኦ ያበረከቱ” ሲል ዩኒቨርስቲው አድናቆቱን በሚገባ ገልጿል።
የተከበሩ አባታቸው አባ መንገሻ ገነሜ (ቀደም ሲል ፊታውራሪ) የግርማዊ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዘመድ ነበሩ። እናታቸው ወይዘሮ ተዋበች ዛማኑኤል በወራሪው ፋሽስት በግፍ ታሥረው በተወሰዱበት ኢጣልያ አገር ውስጥ ሕይወታቸው አለፏል።
አክስታቸው ወ/ሮ ሉልአደይ ዛማኑኤል ልጅ የወንደሰንን እና ታናሽ እህቶቻቸውን ወ/ሪት ኮከቤ መንገሻን እና ወ/ሮ እግዚሐርያ መንገሻን እንደ ልጆቻቸው በፍቅር አሳድገዋቸዋል። ልጅ ከበደ ኃይሌ ታላቅ ወንድማቸው ነበሩ።
ልጅ የወንድወሰን የአንደኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በተፈሪ መኮንን እና በፕሪንቺፔ ዲ ፒያሞንቴ ትምህርት ቤቶች ከተማሩ በኋላ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን አቃቂ በሚገኘው የአድቬንቲስት ሚሲዮን እና አዲስ አበባ በሚገኘው ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ተምረው አጠናቅቀዋል። ቀጥሎም፣ በጊዜው የላንደን ዩኒቨርሲቲ አካል የነበረው ሳውዝሃምፕተን ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ ተቀብሏቸው በኢትዮጵያ መንግሥት የነፃ ትምህርት ዕድል ድጋፍ ተምረው እ ኤ አ በ 1U54 ዓም በኢኮኖሚክስ እና አካውንቲንግ በከፍተኛ ማዕርግ ተመረቁ። ኮሌጅ የተማረ የመጀመሪያው የቤተሰቡ አባል እንደመሆናቸው መጠን ወደ እናት አገራቸው ሲመለሱ ሌሎችን ለመርዳት ይጓጉ ነበር። እውቀታቸውን እና ተሞክሯቸውን ለማስፋት ወደ አሜሪካ ሲጓዙ አስፈላጊው ገንዘብ ስላልነበራቸው ቦስተን ለመድረስ ወደካናዳ በሚጓዝ አንስተኛ የውቅያኖስ መስመር ላይ በአስተናጋጅነት በመሥራት ሃሳባቸውን አሳክተዋል። ከእዚያም እ ኤ አ በ1U5G ዓም ከሐርቫርድ ዩኒቨርሲቲ በኤም ቢ ኤ (MBA) ዲግሪ ተመረቁ።
ልጅ የወንድወሰን መንገሻ ወደ ኢትዮጵያ ከመመለሳቸው በፊት ዶክተር አልበርት ሸቫይጸርን ለማግኘት ምዕራብ መካከለኛው አፍሪቃ ውስጥ ሩቅ ሥፍራ ወደሚገኝ ሆስፒታል ተጓዙ። ሆስፒታሉ ውስጥ ሁለት ሳምንታት ከቆዩ በኋላ ዶክተር ሸቫይጸርን የመሰለ ሌሎችን ለመርዳት የወሰኑ ሰውን መተዋወቅ ለወጣቱ ምሩቅ ታላቅ ክብር ነበር። በሆስፒታሉ ያጋጠማቸው ተሞክሮ በአገራቸው ሕዝብ ሕይወት ላይ ለውጥ ለማምጣት እራሳቸውም በቁርጠኝነት እንዲሰለፉ አድርጓቸዋል።
ወደ የሚወዷት አገራቸው ከተመለሱ በኋላ የመጀመሪያ ሥራ ምድባቸው በኢትዮጵያ አየር
መንገድ የከፍተኛ ማኔጅመንት ኃላፊነት ነበር። ቀጥሎም በገንዘብ ሚንስቴር የዳይሬክተርነት ሹመት አገኙ። በዚሁ ሥራቸው ላይ እንዳሉም በወቅቱ በልዑል ራሥ መንገሻ ሥዩም በሚመራው የኢትዮዽያ የአየር መንገድ ቦርድ አባል በመሆን አየር መንገዱ በተለይ አፍሪቃ ውስጥ በተሳካ ሁኔታ የተለያዩ የብሪያ መስመሮችን እንዲዘረጋ የአባልነታቸውን አስተዋጽኦ አበርክተዎል። የመጀመሪያዎቹን ቦይንግ ጄት አኤሮፕላኖች ለመግዛት በተደረገው ወሳኝ ድርድር ውስጥ ቁልፍ ሚና ነበራቸው።
በ1UG0 የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ምክትል ገዥ ሆነው ተሾሙ
ይህንን የተከበረ ቦታ ለመያዝ የመጀመሪያው ኢትዮጵያዊ ነበሩ። የባንኩን ተቋም ለማዘመን ጠቃሚ ተነሳሽነቶችን በመምራት እና በማስተባበር ለአሥራ አራት ዓመታት በዚያ ሥራ ላይ ቆይተዋል።
ከብዙ ትሩፋቶቻቸው አንዱ የብሔራዊ ባንክ ሠራተኞችን ለተጨማሪ ሥልጠና ወደ ውጭ አገር ለመላክ ያደረጉት ብርቱ ጥረት እና ስኬታማ ተነሳሽነት ነበር።
ይህ በአርቆ አሳቢነት ላይ የተመሠረተ ጥረት ቁጥራቸው እየጨመረ ለመጣው ልዩ የባንክ ሥራ መደቦች በሙያው የሠለጠኑ ኢትዮጵያውያን እና ኢትዮጵያውያትን መመደብ አስችሏል።
ልጅ የወንድወሰን መንገሻ የኢትዮጵያ መንግሥትን ወክለው ከሌሎች ሀገሮች የገንዘብ ሚኒስትሮች ጋር በመተባበር በዓለም አቀፍ የባንክ ማኅበረሰብ ውስጥ ንቁ ተሳትፎ አድርገዋል።
በተለይም ልጅ የወንድወሰን መንገሻ የአፍሪቃን ኤኮኖሚ ለማሳደግ እና ድህነትን ለመቀነስ የታለመውን የአፍሪቃ ልማት ባንክን (AfDB) በሚመሠረትበት ጊዜ ቁልፍ ሚና ተጫውተዋል።
ኢትዮጵያ መሥራች ባለአክሲዮን እንደመሆኗ መጠን ባንኩን በማቋቋም ረገድ ግንባር ቀደም እና ስኬታማ መሪነት አሳይታለች። ብዙዎች ይህንን ስኬት የብሔራዊ ባንክ ገዥ የአቶ ምናሴ ለማ እና ምክትል ገዥ የልጅ የወንድወሰን መንገሻ አርቆ አስተዋይነት እና አመራር ውጤት ነው ብለው ይመለከቱታል።
በዓለም አቀፍ ፋይናንስ ላይ በነበራቸው ዕውቀት እና ባለራዕይ አመራር በ1U80ዎቹ ዓመታት አፍሪቃ ልማት ባንክ ካፒታሉን ለማሳደግ ክልላዊ ያልሆኑ ሀገራትም
(non-regional countries) እንዲሳተፉ መንገድ ከፍተዋል። ይህም ዛሬ የባንኩ የስኬት ታሪክ ነው።
ትጉህ እና ድንቅ አትዮጵያዊው ልጅ የወንድወሰን መንገሻ በባልደረቦቻቸው እና በመንግስት ከፍተኛ ባለሥልጣናት ዘንድ ሰፊ ክብር ያሰጡዋቸው አዕምሯዊ ችሎታቸው፣ የሀገራቸውን እድገት ለማፋጠን ያሳዩት ቁርጠኝነት እና ከሌሎች ጋር ተስማምቶ የመሥራት ችሎታቸው። ግርማዊ ንጉሠ ነገሥት የልጅ የወንድወሰን መንገሻን የአመራር ችሎታቸውን እና ለፍትሃዊነት ያላቸውን ጥልቀት በመመዘን የቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ የሽልማት ድርጅት አምስት ባለአደራዎች ውስጥ አንዱ አድርገው ሾመዋቸዋል። በዚህም ኃላፊነት ከአስር ዓመታት በላይ አገልግለዋል።
ልጅ የወንድወሰን መንገሻ እ ኤ አ 1U74 ዓም በሚያዝያ ወር ዋሽንግተን ዲሲ በተካሄደው የአይ ኤም ኤፍ (IMF) ስብሰባ በመሳተፍ ላይ እንዳሉ በኢትዮጵያ የነበረው ሁኔታ አደገኛ እየሆነ መጣ። ሁኔታው እርሳቸውንና ሌሎች በሺዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያንን ከሚወዷት ሀገራቸው የለያቸው እና ማለቂያ የሌለው የመሰለው አሳዛኝ የግዳጅ ግዞት ዘመን መጀመሪያ ነበር።
ባለቤታቸው እና ሦስቱም ልጆቻቸው ከእርሳቸው ጋር ለመሆን ወደ አሜሪካ መጓዝ ቻሉ። ልጅ የወንድወሰን ወደ ኢትዮጵያ መመለስ ጥሩ አማራጭ እንዳልሆነ ከተረዱ በኋላ ቅድሚያ የሰጡት ቤተሰቡን የሚያስተዳድሩበት በተለይም ልጆቻቸውን ለማስተማር የሚያስችል ሥራ መፈለጉን ነበር።
በዓለም አቀፍ ፋይናንስ መስክ በነበራቸው ሰፊ ዕውቀት እና ችሎታ ለንደን በሚገኘው First Boston Corporation (ፈርስት ቦስተን ኮርፖሬሽን) ሥራ ለማግኘት በቁ። ቀጥሎም በታማኝነታቸው እና በልዩ ችሎታቸው ወደ ማኔጂንግ ዳይሬክተርነት (Managing Director) ደረጃ ዕድገት አገኙ።
በኩባንያው ውስጥ ለብዙ ዓመታት በጥሩ መሪነት ከአገለገሉ በኃላ Associated African Financial Services (አሶሽየትድ አፍሪካን ፋይናንሽያል ሰርቪስስ) የሚባል የአማካሪ ድርጅት አቌቁመው በተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት ጉልህ በሆኑ ፕሮጀክቶች ላይ ከአሥር አመታት በላይ ሠርተዋል።
ልጅ የወንድወሰን መንገሻ በቀሪው ሕይወታቸውም እንደሁልጊዜው ሌሎችን ለመርዳት፣ ሀገራቸው እና ሕዝቡ ላደረገላቸው ውለታ ለመመለስ ትኩረት በማድረጋቸው ብዙ የበጎ አድራጎት ቡድኖችን፣ ቤተክርስቲያናትን እና ግለ ሰቦችን ከመርዳት ተቆጥበው አያውቁም። ቤቱ ይቁጠረው እንደሚባለው ሰው የማያውቀው አምላክ ግን የሚያየው ብዙ ችግረኛችን ደግፈዋል።
በተለይ ኅብረተሰቡን ለመርዳት ካቋቋሙዎቸው ቅርሶች አንዱ ለውድ አባታቸው መታሰቢያ እንዲሆን ባሕር ዳር ውስጥ የከፈቱት “አባ መንገሻ ገነሜ የሕዝብ ቤተ መጻሕፍት እና የመረጃ ማዕከል” ነው።
ወጣቶች ትምህርታቸውን በትጋት እንዲቀጥሉ እና በሙሉ አቅማቸው ዓላማቸውን ለማሳካት እንዲጥሩ ለማበረታታት እና ለመደገፍ በምንም ዓይነት ወደኃላ አዩሉም ነበር።
በተለይም ለከፍተኛ ትምህርት እድሎችን ለማስፋት ከነበራቸው ጽኑ ፍላጎት በራሳቸው እና በባለቤታቸው ወይዘሮ ሕይወት ስም በሃርቫርድ ቢዝነስ ትምህርት ቤት የትምህርት ብቃት ላላቸው የአፍሪቃውያን ተማሪዎች ስኮላርሺፕ አቋቀቁመው ብዙ ተማሪዋች ሊጠቅሙ ችለዎል።
በፍቅር ወንድዬ ተብለው የሚጠሩትን ልጅ የወንድወሰን መንገሻን የማወቅ ዕድል ያገኙ ሁሉ ተንከባካቢነታቸውን፣ ትሁትነታቸውን እና ለጋሥነታቸውን ይመሰክራሉ። ዘመዶችን፣ ጓደኞችን እንዲሁም ሌሎች ሰዎች መርዳት እና ምክር በመለገስ ረገድ የተቻላቸውን ሁሉ አድርገዋል። እንዲሁም ታዳጊ እና ወጣት የሆኑት ዘመዶቻቸው እንደአባት እና አማካሪ ያዩዋቸው ነበር።
የቤተሰብ አባላት ታማኝነታቸውን እና ጥበባዊ ምክራቸውን ከፍ አድርገው ይመለከቷቸው ነበር። በተለይም የቅርብ ዘመዶቻቸው ከሆኑት ከራሥ አንዳርጋቸው መሳይ እና ከልዕልት ተናኘወርቅ ኃይለ ሥላሴ ፍቅር እና አክብሮት ምንግዜም አልተላያቸውም።
ልጅ የወንድወሰን እ ኤ አ ጥቅምት 12 ቀን 2025 በሎንዶን በሚገኘው ቤታቸው በቤተሰብ ተከበው በሰላም በማረፍ ከዚህ ዓለም ተለይተዋል።
በነሐሴ 23 ቀን 1964 ዓም እኤአ በትዳር ካገቧቸው ከውድ ባለቤታቸው ከወ/ሮ ሕይወት ግሬታ መንገሻ ጋር በፍቅር፣ በመከባበር እና በተድላ የዕድሜ ባለፀጋ ሆነው ያሬድ፣ ያድዋ እና የአደይን አፍርተዋል።
የሰባት የልጅ ልጆች አያት ለመሆን በቅተዋል - ካሌብ፣ ሶፊያ፣ ሉላዴይ (ሊሊ)፣ ጌሊላ፣ አሸር፣ ፀጋ እና ኢያሱ ። ቤተሰቡ መሪ አባት የነበሩትን በሞት በማጣታቸው በታላቅ ሀዘን ላይ ቢወድቁም አምላክ ረጅም ዕድሜ ስለሰጣቸው እና ቤተሰቡን ፍቅር በተሞላበት አርአያነት በመምራታቸው በምስጋና ተሞልተዋል።
እኚህ ትሁት የኢየሱስ ክርስቶስ አገልጋይ ፣ ቅዱስ ጳውሎስ በ1ኛ ቆሮንቶስ 13 ላይ እንዳስተማረው የፍቅር ምሳሌ ሆነው ኖረዋል።
“ፍቅር ታጋሽ ነው፣ ፍቅር ደግ ነው፣ ፍቅር አይመቀኝም፣ ፍቅር አይታበይም፣ ፍቅር አይኰራም፣
ፍቅር ስነስርዓተቢስ አይደለም፣ ፍቅር የራሱን ጥቅም ብቻ ፈላጊ አይደለም፣ ፍቅር አይበሳጭም፣ ፍቅር ቢበደልም እንኳ በደልን እንደበደል አይቆጥርም፣ ፍቅር እውነት በሆነ ነገር ይደሰታል እንጂ ክፋት በሆነ ነገር አይደሰትም፣ ፍቅር ሁሉን ችሎ ይታገሳል፣ ፍቅር በሁሉም ላይ ተስፋ የደርጋል፣ ፍቅር በሁሉም ነገር ይጸናል”
ቸሩ አምላክ ነፍሳቸውን የዘላለም እረፍት ይስጥልን።
ዕዝራ እጅጉ-(ተወዳጅ ሚድያ)
ታሕሣስ 24 ቀን 1920 ዓም - ጥቅምት 2 ቀን 2018 ዓ.ም
ቀብራቸው ሐሙስ ጥቅምት 13 በለንደን ይፈፀማል
#ethiopia | ተወዳጅ ሚድያ እና ኮምዩኒኬሽን ፣ መዝገበ-አእምሮ ( የአማርኛ ኢንሳይክሎፒዲያ ) ፕሮጀክቱ ለአገር የሠሩ ሰዎችን ታሪክ እየሰነደ እንደሆነ ይታወቃል። ይህ ታሪክ በዲጂታል ሚድያዎች ፣በመፅሀፍ፣በድምፅ ትረካና በሌሎችም መንገዶች እየቀረበ እንደሆነ ይታወቃል። ባለፉት 4 ዓመት ከ 5 ወር ጊዜ ውስጥ የ423 ሰዎችን የሕይወትና የሥራ ታሪክ ለመሰነድ የቻልን ሲሆን 600 ገፅ ባላቸው ሁለት የተለያዩ መፅሐፎች ላይም ታሪኮቹ ዘመን ተሻጋሪ ሆነው እንዲቀመጡ አድርገናል።
ቅፅ 3 መዝገበ አእምሮ ከ20 በላይ ዘርፎች ይኖሩታል። እዚህ ዘርፍ ውስጥ የሚገኙ የአገር ባለውለታዎችን መሰነዳችን ይቀጥላል። የባንክ፣ የፋይናንስ እና የኢንሹራንስ በሚለው ዘርፍ ውስጥ ታሪካቸው የሚሰነደው ልጅ የወንድወሰን መንገሻ ሲሆኑ ታሪካቸውንም ዕዝራ እጅጉ ሰንዶታል።
የሐርቫርድ ዩኒቨርሲቲ የግራጅዌት ቢዝነስ ትምህርት ቤት የታላቅ አገልግሎት እና ለቀድሞ ተማሪዎች የሥራ ስኬት ተብሎ የተሰየመውን ሽልማት ለልጅ የወንድወሰን መንገሻ እ ኤ አ በ1996 ዓ.ም ሲሰጣቸው በመጀመሪያ የእርሳቸውን ማንነት መገለጫ ያደረገው “ሰብዓዊነትን የረዱ” በማለት እና በምስጋናው መዝጊያ ላይ ደግሞ “ለዓለም ደህንነት የታቻላቸውን አስተዋጽኦ ያበረከቱ” ሲል ዩኒቨርሲቲው አድናቆቱን በሚገባ ገልጿል።
የተከበሩ አባታቸው አባ መንገሻ ገነሜ (ቀደም ሲል ፊታውራሪ) የግርማዊ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዘመድ ነበሩ። እናታቸው ወይዘሮ ተዋበች ዛማኑኤል በወራሪው ፋሽስት በግፍ ታስረው በተወሰዱበት ኢጣልያ አገር ውስጥ ሕይወታቸው አልፏል። አክስታቸው ወ/ሮ ሉልአደይ ዛማኑኤል ልጅ የወንደሰንን እና ታናሽ እህቶቻቸውን ወ/ሪት ኮከቤ መንገሻን እና ወ/ሮ እግዚሐርያ መንገሻን እንደ ልጆቻቸው በፍቅር አሳድገዋቸዋል። ልጅ ከበደ ኃይሌ ታላቅ ወንድማቸው ነበሩ።
ልጅ የወንድወሰን የአንደኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በተፈሪ መኮንን እና በፕሪንቺፔ ዲ ፒያሞንቴ ትምህርት ቤቶች ከተማሩ በኋላ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን አቃቂ በሚገኘው የአድቬንቲስት ሚሲዮን እና አዲስ አበባ በሚገኘው ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ተምረው አጠናቅቀዋል። ቀጥሎም፣ በጊዜው የሎንዶን ዩኒቨርሲቲ አካል የነበረው ሳውዝሃምፕተን ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ ተቀብሏቸው በኢትዮጵያ መንግሥት የነፃ ትምህርት ዕድል ድጋፍ ተምረው እ ኤ አ በ1954 ዓ.ም በኢኮኖሚክስ እና አካውንቲንግ በከፍተኛ ማዕረግ ተመረቁ። ኮሌጅ የተማረ የመጀመሪያው የቤተሰቡ አባል እንደመሆናቸው መጠን ወደ እናት አገራቸው ሲመለሱ ሌሎችን ለመርዳት ይጓጉ ነበር። እውቀታቸውን እና ተሞክሯቸውን ለማስፋት ወደ አሜሪካ ሲጓዙ አስፈላጊው ገንዘብ ስላልነበራቸው ቦስተን ለመድረስ ወደካናዳ በሚጓዝ አንስተኛ የውቅያኖስ መስመር ላይ በአስተናጋጅነት በመሥራት ሀሳባቸውን አሳክተዋል። ከእዚያም እ ኤ አ በ1956 ዓ.ም ከሐርቫርድ ዩኒቨርሲቲ በኤም ቢ ኤ (MBA) ዲግሪ ተመረቁ።
ልጅ የወንድወሰን መንገሻ ፣ወደ ኢትዮጵያ ከመመለሳቸው በፊት ዶክተር አልበርት ሸቫይጸርን ለማግኘት ምዕራብ መካከለኛው አፍሪቃ ውስጥ ሩቅ ሥፍራ ወደሚገኝ ሆስፒታል ተጓዙ። ሆስፒታሉ ውስጥ ሁለት ሳምንታት ከቆዩ በኋላ ዶክተር ሸቫይጸርን የመሰለ ሌሎችን ለመርዳት የወሰኑ ሰውን መተዋወቅ ለወጣቱ ምሩቅ ታላቅ ክብር ነበር። በሆስፒታሉ ያጋጠማቸው ተሞክሮ በአገራቸው ሕዝብ ሕይወት ላይ ለውጥ ለማምጣት እራሳቸውም በቁርጠኝነት እንዲሰለፉ አድርጓቸዋል።
ወደ የሚወዷት አገራቸው ከተመለሱ በኋላ የመጀመሪያ ሥራ ምድባቸው በኢትዮጵያ አየር መንገድ የከፍተኛ ማኔጅመንት ኃላፊነት ነበር። ቀጥሎም በገንዘብ ሚንስቴር የዳይሬክተርነት ሹመት አገኙ። በዚሁ ሥራቸው ላይ እንዳሉም በወቅቱ በልዑል ራሥ መንገሻ ሥዩም በሚመራው የኢትዮዽያ የአየር መንገድ ቦርድ አባል በመሆን አየር መንገዱ በተለይ አፍሪቃ ውስጥ በተሳካ ሁኔታ የተለያዩ የብሪያ መስመሮችን እንዲዘረጋ የአባልነታቸውን አስተዋጽኦ አበርክተዎል። የመጀመሪያዎቹን ቦይንግ ጄት ኤሮፕላኖች ለመግዛት በተደረገው ወሳኝ ድርድር ውስጥ ቁልፍ ሚና ነበራቸው።
በ1960 የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ምክትል ገዥ ሆነው ተሾሙ። ይህንን የተከበረ ቦታ ለመያዝ የመጀመሪያው ኢትዮጵያዊ ነበሩ። የባንኩን ተቋም ለማዘመን ጠቃሚ ተነሳሽነቶችን በመምራት እና በማስተባበር ለአሥራ አራት ዓመታት በዚያ ሥራ ላይ ቆይተዋል። ከብዙ ትሩፋቶቻቸው አንዱ የብሔራዊ ባንክ ሠራተኞችን ለተጨማሪ ሥልጠና ወደ ውጭ አገር ለመላክ ያደረጉት ብርቱ ጥረት እና ስኬታማ ተነሳሽነት ነበር። ይህ በአርቆ አሳቢነት ላይ የተመሠረተ ጥረት ቁጥራቸው እየጨመረ ለመጣው ልዩ የባንክ ሥራ መደቦች በሙያው የሠለጠኑ ኢትዮጵያውያን እና ኢትዮጵያውያትን መመደብ አስችሏል።
ልጅ የወንድወሰን መንገሻ የኢትዮጵያ መንግሥትን ወክለው ከሌሎች ሀገሮች የገንዘብ ሚኒስትሮች ጋር በመተባበር በዓለም አቀፍ የባንክ ማኅበረሰብ ውስጥ ንቁ ተሳትፎ አድርገዋል። በተለይም ልጅ የወንድወሰን መንገሻ የአፍሪቃን ኤኮኖሚ ለማሳደግ እና ድህነትን ለመቀነስ የታለመውን የአፍሪቃ ልማት ባንክን (AfDB) በሚመሠረትበት ጊዜ ቁልፍ ሚና ተጫውተዋል። ኢትዮጵያ መሥራች ባለአክሲዮን እንደመሆኗ መጠን ባንኩን በማቋቋም ረገድ ግንባር ቀደም እና ስኬታማ መሪነት አሳይታለች። ብዙዎች ይህንን ስኬት የብሔራዊ ባንክ ገዥ የአቶ ምናሴ ለማ እና ምክትል ገዥ የልጅ የወንድወሰን መንገሻ አርቆ አስተዋይነት እና አመራር ውጤት ነው ብለው ይመለከቱታል። በዓለም አቀፍ ፋይናንስ ላይ በነበራቸው ዕውቀት እና ባለራዕይ አመራር በ1980 ዎቹ ዓመታት አፍሪቃ ልማት ባንክ ካፒታሉን ለማሳደግ ክልላዊ ያልሆኑ ሀገራትም
(non-regional countries) እንዲሳተፉ መንገድ ከፍተዋል። ይህም ዛሬ የባንኩ የስኬት ታሪክ ነው።
ትጉህ እና ድንቅ አትዮጵያዊው ልጅ የወንድወሰን መንገሻ በባልደረቦቻቸው እና በመንግስት ከፍተኛ ባለሥልጣናት ዘንድ ሰፊ ክብር ያሰጡዋቸው አዕምሯዊ ችሎታቸው፣ የሀገራቸውን እድገት ለማፋጠን ያሳዩት ቁርጠኝነት እና ከሌሎች ጋር ተስማምቶ የመሥራት ችሎታቸው። ግርማዊ ንጉሠ ነገሥት የልጅ የወንድወሰን መንገሻን የአመራር ችሎታቸውን እና ለፍትሃዊነት ያላቸውን ጥልቀት በመመዘን የቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ የሽልማት ድርጅት አምስት ባለአደራዎች ውስጥ አንዱ አድርገው ሾመዋቸዋል። በዚህም ኃላፊነት ከ10 ዓመታት በላይ አገልግለዋል።
ልጅ የወንድወሰን መንገሻ እ ኤ አ 1974 ዓም በሚያዝያ ወር ዋሽንግተን ዲሲ በተካሄደው የአይ ኤም ኤፍ (IMF) ስብሰባ በመሳተፍ ላይ እንዳሉ በኢትዮጵያ የነበረው ሁኔታ አደገኛ እየሆነ መጣ። ሁኔታው እርሳቸውንና ሌሎች በሺዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያንን ከሚወዷት ሀገራቸው የለያቸው እና ማለቂያ የሌለው የመሰለው አሳዛኝ የግዳጅ ግዞት ዘመን መጀመሪያ ነበር። ባለቤታቸው እና ሦስቱም ልጆቻቸው ከእርሳቸው ጋር ለመሆን ወደ አሜሪካ መጓዝ ቻሉ። ልጅ የወንድወሰን ወደ ኢትዮጵያ መመለስ ጥሩ አማራጭ እንዳልሆነ ከተረዱ በኋላ ቅድሚያ የሰጡት ቤተሰቡን የሚያስተዳድሩበት በተለይም ልጆቻቸውን ለማስተማር የሚያስችል ሥራ መፈለጉን ነበር።
በዓለም አቀፍ ፋይናንስ መስክ በነበራቸው ሰፊ ዕውቀት እና ችሎታ ለንደን በሚገኘው First Boston Corporation (ፈርስት ቦስተን ኮርፖሬሽን) ሥራ ለማግኘት በቁ። ቀጥሎም በታማኝነታቸው እና በልዩ ችሎታቸው ወደ ማኔጂንግ ዳይሬክተርነት (Managing Director)
ደረጃ ዕድገት አገኙ። በኩባንያው ውስጥ ለብዙ ዓመታት በጥሩ መሪነት ከአገለገሉ በኃላ Associated African Financial Services (አሶሽየትድ አፍሪካን ፋይናንሽያል ሰርቪስስ) የሚባል የአማካሪ ድርጅት አቌቁመው በተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት ጉልህ በሆኑ ፕሮጀክቶች ላይ ከአሥር አመታት በላይ ሠርተዋል።
ልጅ የወንድወሰን መንገሻ በቀሪው ሕይወታቸውም እንደሁልጊዜው ሌሎችን ለመርዳት፣ ሀገራቸው እና ሕዝቡ ላደረገላቸው ውለታ ለመመለስ ትኩረት በማድረጋቸው ብዙ የበጎ አድራጎት ቡድኖችን፣ ቤተክርስቲያናትን እና ግለ ሰቦችን ከመርዳት ተቆጥበው አያውቁም። ቤቱ ይቁጠረው እንደሚባለው ሰው የማያውቀው አምላክ ግን የሚያየው ብዙ ችግረኛችን ደግፈዋል። በተለይ ኅብረተሰቡን ለመርዳት ካቋቋሙዎቸው ቅርሶች አንዱ ለውድ አባታቸው መታሰቢያ እንዲሆን ባሕር ዳር ውስጥ የከፈቱት “አባ መንገሻ ገነሜ የሕዝብ ቤተ መጻሕፍት እና የመረጃ ማዕከል” ነው።
ወጣቶች ትምህርታቸውን በትጋት እንዲቀጥሉ እና በሙሉ አቅማቸው ዓላማቸውን ለማሳካት እንዲጥሩ ለማበረታታት እና ለመደገፍ በምንም ዓይነት ወደኃላ አዩሉም ነበር። በተለይም ለከፍተኛ ትምህርት እድሎችን ለማስፋት ከነበራቸው ጽኑ ፍላጎት በራሳቸው እና በባለቤታቸው ወይዘሮ ሕይወት ስም በሃርቫርድ ቢዝነስ ትምህርት ቤት የትምህርት ብቃት ላላቸው የአፍሪቃውያን ተማሪዎች ስኮላርሺፕ አቋቀቁመው ብዙ ተማሪዋች ሊጠቅሙ ችለዎል።
በፍቅር ወንድዬ ተብለው የሚጠሩትን ልጅ የወንድወሰን መንገሻን የማወቅ ዕድል ያገኙ ሁሉ ተንከባካቢነታቸውን፣ ትሁትነታቸውን እና ለጋሥነታቸውን ይመሰክራሉ። ዘመዶችን፣ ጓደኞችን እንዲሁም ሌሎች ሰዎች መርዳት እና ምክር በመለገስ ረገድ የተቻላቸውን ሁሉ አድርገዋል። እንዲሁም ታዳጊ እና ወጣት የሆኑት ዘመዶቻቸው እንደአባት እና አማካሪ ያዩዋቸው ነበር። የቤተሰብ አባላት ታማኝነታቸውን እና ጥበባዊ ምክራቸውን ከፍ አድርገው ይመለከቷቸው ነበር። በተለይም የቅርብ ዘመዶቻቸው ከሆኑት ከራሥ አንዳርጋቸው መሳይ እና ከልዕልት ተናኘወርቅ ኃይለ ሥላሴ ፍቅር እና አክብሮት ምንግዜም አልተላያቸውም።
ልጅ የወንድወሰን እ ኤ አ ጥቅምት 12 ቀን 2025 በለንደን በሚገኘው ቤታቸው በቤተሰብ ተከበው በሰላም በማረፍ ከዚህ አለም ተለይተዋል።
በነሐሴ 23 ቀን 1UG4 ዓም እኤአ በትዳር ካገቡዋቸው ከውድ ባለቤታቸው ከወ/ሮ ሕይወት ጋር በፍቅር፣ በመከባበር እና በተድላ የዕድሜ ባለፀጋ ሆነው ያሬድ፣ ያድዋ እና የአደይን አፍርተዋል። የሰባት የልጅ ልጆች አያት ለመሆን በቅተዋል - ካሌብ፣ ሶፊያ፣ ሉላዴይ (ሊሊ)፣ ጌሊላ፣ አሸር፣ ፀጋ እና ኢያሱ ። ቤተሰቡ መሪ አባት የነበሩትን በሞት በማጣታቸው በታላቅ ሀዘን ላይ ቢወድቁም አምላክ ረጅም ዕድሜ ስለሰጣቸው እና ቤተሰቡን ፍቅር በተሞላበት አርአያነት በመምራታቸው በምስጋና ተሞልተዋል።
እኚህ ትሁት የኢየሱስ ክርስቶስ አገልጋይ ፣ ቅዱስ ጳውሎስ በ1ኛ ቆሮንቶስ 13 ላይ እንዳስተማረው የፍቅር ምሳሌ ሆነው ኖረዋል።
“ፍቅር ታጋሽ ነው፣ ፍቅር ደግ ነው፣ ፍቅር አይመቀኝም፣ ፍቅር አይታበይም፣ ፍቅር አይኰራም፣ ፍቅር ስነስርዓተቢስ አይደለም፣ ፍቅር የራሱን ጥቅም ብቻ ፈላጊ አይደለም፣ ፍቅር አይበሳጭም፣ ፍቅር ቢበደልም እንኳ በደልን እንደበደል አይቆጥርም፣ ፍቅር እውነት በሆነ ነገር ይደሰታል እንጂ ክፋት በሆነ ነገር አይደሰትም፣ ፍቅር ሁሉን ችሎ ይታገሳል፣ ፍቅር በሁሉም ላይ ተስፋ የደርጋል፣ ፍቅር በሁሉም ነገር ይጸናል”
ቸሩ አምላክ ነፍሳቸውን የዘላለም እረፍት ይስጥልን።
ቤተሰቡ ጓደኞቻቸው እና ዘመዶቻቸው ለላኩት አጽናኝ መልእክቶች እና የሀዘን መግለጫዎች ሁሉ ልባዊ ምስጋናቸውን ያቀርባሉ።ልጅ የወንድወሰን መንገሻ
ታሕሣስ 24 ቀን 1U20 ዓም - ጥቅምት 2 ቀን 2018 ዓም
የሐርቫርድ ዩኒቨርሲቲ የግራጅዌት ቢዝነስ ትምህርት ቤት የታላቅ አገልግሎት እና ለቀድሞ ተማሪዎች የሥራ ስኬት ተብሎ የተሰየመውን ሽልማት ለልጅ የወንድወሰን መንገሻ እ ኤ አ በ1UUG ዓም ሲሰጣቸው በመጀመሪያ የሳቸውን ማንነት መገለጫ ያደረገው “ሰብዓዊነትን የረዱ” በማለት እና በምስጋናው መዝጊያ ላይ ደግሞ “ለዓለም ደህንነት የታቻላቸውን አስተዋጽኦ ያበረከቱ” ሲል ዩኒቨርስቲው አድናቆቱን በሚገባ ገልጿል።
የተከበሩ አባታቸው አባ መንገሻ ገነሜ (ቀደም ሲል ፊታውራሪ) የግርማዊ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዘመድ ነበሩ። እናታቸው ወይዘሮ ተዋበች ዛማኑኤል በወራሪው ፋሽስት በግፍ ታሥረው በተወሰዱበት ኢጣልያ አገር ውስጥ ሕይወታቸው አለፏል።
አክስታቸው ወ/ሮ ሉልአደይ ዛማኑኤል ልጅ የወንደሰንን እና ታናሽ እህቶቻቸውን ወ/ሪት ኮከቤ መንገሻን እና ወ/ሮ እግዚሐርያ መንገሻን እንደ ልጆቻቸው በፍቅር አሳድገዋቸዋል። ልጅ ከበደ ኃይሌ ታላቅ ወንድማቸው ነበሩ።
ልጅ የወንድወሰን የአንደኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በተፈሪ መኮንን እና በፕሪንቺፔ ዲ ፒያሞንቴ ትምህርት ቤቶች ከተማሩ በኋላ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን አቃቂ በሚገኘው የአድቬንቲስት ሚሲዮን እና አዲስ አበባ በሚገኘው ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ተምረው አጠናቅቀዋል። ቀጥሎም፣ በጊዜው የላንደን ዩኒቨርሲቲ አካል የነበረው ሳውዝሃምፕተን ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ ተቀብሏቸው በኢትዮጵያ መንግሥት የነፃ ትምህርት ዕድል ድጋፍ ተምረው እ ኤ አ በ 1U54 ዓም በኢኮኖሚክስ እና አካውንቲንግ በከፍተኛ ማዕርግ ተመረቁ። ኮሌጅ የተማረ የመጀመሪያው የቤተሰቡ አባል እንደመሆናቸው መጠን ወደ እናት አገራቸው ሲመለሱ ሌሎችን ለመርዳት ይጓጉ ነበር። እውቀታቸውን እና ተሞክሯቸውን ለማስፋት ወደ አሜሪካ ሲጓዙ አስፈላጊው ገንዘብ ስላልነበራቸው ቦስተን ለመድረስ ወደካናዳ በሚጓዝ አንስተኛ የውቅያኖስ መስመር ላይ በአስተናጋጅነት በመሥራት ሃሳባቸውን አሳክተዋል። ከእዚያም እ ኤ አ በ1U5G ዓም ከሐርቫርድ ዩኒቨርሲቲ በኤም ቢ ኤ (MBA) ዲግሪ ተመረቁ።
ልጅ የወንድወሰን መንገሻ ወደ ኢትዮጵያ ከመመለሳቸው በፊት ዶክተር አልበርት ሸቫይጸርን ለማግኘት ምዕራብ መካከለኛው አፍሪቃ ውስጥ ሩቅ ሥፍራ ወደሚገኝ ሆስፒታል ተጓዙ። ሆስፒታሉ ውስጥ ሁለት ሳምንታት ከቆዩ በኋላ ዶክተር ሸቫይጸርን የመሰለ ሌሎችን ለመርዳት የወሰኑ ሰውን መተዋወቅ ለወጣቱ ምሩቅ ታላቅ ክብር ነበር። በሆስፒታሉ ያጋጠማቸው ተሞክሮ በአገራቸው ሕዝብ ሕይወት ላይ ለውጥ ለማምጣት እራሳቸውም በቁርጠኝነት እንዲሰለፉ አድርጓቸዋል።
ወደ የሚወዷት አገራቸው ከተመለሱ በኋላ የመጀመሪያ ሥራ ምድባቸው በኢትዮጵያ አየር
መንገድ የከፍተኛ ማኔጅመንት ኃላፊነት ነበር። ቀጥሎም በገንዘብ ሚንስቴር የዳይሬክተርነት ሹመት አገኙ። በዚሁ ሥራቸው ላይ እንዳሉም በወቅቱ በልዑል ራሥ መንገሻ ሥዩም በሚመራው የኢትዮዽያ የአየር መንገድ ቦርድ አባል በመሆን አየር መንገዱ በተለይ አፍሪቃ ውስጥ በተሳካ ሁኔታ የተለያዩ የብሪያ መስመሮችን እንዲዘረጋ የአባልነታቸውን አስተዋጽኦ አበርክተዎል። የመጀመሪያዎቹን ቦይንግ ጄት አኤሮፕላኖች ለመግዛት በተደረገው ወሳኝ ድርድር ውስጥ ቁልፍ ሚና ነበራቸው።
በ1UG0 የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ምክትል ገዥ ሆነው ተሾሙ
ይህንን የተከበረ ቦታ ለመያዝ የመጀመሪያው ኢትዮጵያዊ ነበሩ። የባንኩን ተቋም ለማዘመን ጠቃሚ ተነሳሽነቶችን በመምራት እና በማስተባበር ለአሥራ አራት ዓመታት በዚያ ሥራ ላይ ቆይተዋል።
ከብዙ ትሩፋቶቻቸው አንዱ የብሔራዊ ባንክ ሠራተኞችን ለተጨማሪ ሥልጠና ወደ ውጭ አገር ለመላክ ያደረጉት ብርቱ ጥረት እና ስኬታማ ተነሳሽነት ነበር።
ይህ በአርቆ አሳቢነት ላይ የተመሠረተ ጥረት ቁጥራቸው እየጨመረ ለመጣው ልዩ የባንክ ሥራ መደቦች በሙያው የሠለጠኑ ኢትዮጵያውያን እና ኢትዮጵያውያትን መመደብ አስችሏል።
ልጅ የወንድወሰን መንገሻ የኢትዮጵያ መንግሥትን ወክለው ከሌሎች ሀገሮች የገንዘብ ሚኒስትሮች ጋር በመተባበር በዓለም አቀፍ የባንክ ማኅበረሰብ ውስጥ ንቁ ተሳትፎ አድርገዋል።
በተለይም ልጅ የወንድወሰን መንገሻ የአፍሪቃን ኤኮኖሚ ለማሳደግ እና ድህነትን ለመቀነስ የታለመውን የአፍሪቃ ልማት ባንክን (AfDB) በሚመሠረትበት ጊዜ ቁልፍ ሚና ተጫውተዋል።
ኢትዮጵያ መሥራች ባለአክሲዮን እንደመሆኗ መጠን ባንኩን በማቋቋም ረገድ ግንባር ቀደም እና ስኬታማ መሪነት አሳይታለች። ብዙዎች ይህንን ስኬት የብሔራዊ ባንክ ገዥ የአቶ ምናሴ ለማ እና ምክትል ገዥ የልጅ የወንድወሰን መንገሻ አርቆ አስተዋይነት እና አመራር ውጤት ነው ብለው ይመለከቱታል።
በዓለም አቀፍ ፋይናንስ ላይ በነበራቸው ዕውቀት እና ባለራዕይ አመራር በ1U80ዎቹ ዓመታት አፍሪቃ ልማት ባንክ ካፒታሉን ለማሳደግ ክልላዊ ያልሆኑ ሀገራትም
(non-regional countries) እንዲሳተፉ መንገድ ከፍተዋል። ይህም ዛሬ የባንኩ የስኬት ታሪክ ነው።
ትጉህ እና ድንቅ አትዮጵያዊው ልጅ የወንድወሰን መንገሻ በባልደረቦቻቸው እና በመንግስት ከፍተኛ ባለሥልጣናት ዘንድ ሰፊ ክብር ያሰጡዋቸው አዕምሯዊ ችሎታቸው፣ የሀገራቸውን እድገት ለማፋጠን ያሳዩት ቁርጠኝነት እና ከሌሎች ጋር ተስማምቶ የመሥራት ችሎታቸው። ግርማዊ ንጉሠ ነገሥት የልጅ የወንድወሰን መንገሻን የአመራር ችሎታቸውን እና ለፍትሃዊነት ያላቸውን ጥልቀት በመመዘን የቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ የሽልማት ድርጅት አምስት ባለአደራዎች ውስጥ አንዱ አድርገው ሾመዋቸዋል። በዚህም ኃላፊነት ከአስር ዓመታት በላይ አገልግለዋል።
ልጅ የወንድወሰን መንገሻ እ ኤ አ 1U74 ዓም በሚያዝያ ወር ዋሽንግተን ዲሲ በተካሄደው የአይ ኤም ኤፍ (IMF) ስብሰባ በመሳተፍ ላይ እንዳሉ በኢትዮጵያ የነበረው ሁኔታ አደገኛ እየሆነ መጣ። ሁኔታው እርሳቸውንና ሌሎች በሺዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያንን ከሚወዷት ሀገራቸው የለያቸው እና ማለቂያ የሌለው የመሰለው አሳዛኝ የግዳጅ ግዞት ዘመን መጀመሪያ ነበር።
ባለቤታቸው እና ሦስቱም ልጆቻቸው ከእርሳቸው ጋር ለመሆን ወደ አሜሪካ መጓዝ ቻሉ። ልጅ የወንድወሰን ወደ ኢትዮጵያ መመለስ ጥሩ አማራጭ እንዳልሆነ ከተረዱ በኋላ ቅድሚያ የሰጡት ቤተሰቡን የሚያስተዳድሩበት በተለይም ልጆቻቸውን ለማስተማር የሚያስችል ሥራ መፈለጉን ነበር።
በዓለም አቀፍ ፋይናንስ መስክ በነበራቸው ሰፊ ዕውቀት እና ችሎታ ለንደን በሚገኘው First Boston Corporation (ፈርስት ቦስተን ኮርፖሬሽን) ሥራ ለማግኘት በቁ። ቀጥሎም በታማኝነታቸው እና በልዩ ችሎታቸው ወደ ማኔጂንግ ዳይሬክተርነት (Managing Director) ደረጃ ዕድገት አገኙ።
በኩባንያው ውስጥ ለብዙ ዓመታት በጥሩ መሪነት ከአገለገሉ በኃላ Associated African Financial Services (አሶሽየትድ አፍሪካን ፋይናንሽያል ሰርቪስስ) የሚባል የአማካሪ ድርጅት አቌቁመው በተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት ጉልህ በሆኑ ፕሮጀክቶች ላይ ከአሥር አመታት በላይ ሠርተዋል።
ልጅ የወንድወሰን መንገሻ በቀሪው ሕይወታቸውም እንደሁልጊዜው ሌሎችን ለመርዳት፣ ሀገራቸው እና ሕዝቡ ላደረገላቸው ውለታ ለመመለስ ትኩረት በማድረጋቸው ብዙ የበጎ አድራጎት ቡድኖችን፣ ቤተክርስቲያናትን እና ግለ ሰቦችን ከመርዳት ተቆጥበው አያውቁም። ቤቱ ይቁጠረው እንደሚባለው ሰው የማያውቀው አምላክ ግን የሚያየው ብዙ ችግረኛችን ደግፈዋል።
በተለይ ኅብረተሰቡን ለመርዳት ካቋቋሙዎቸው ቅርሶች አንዱ ለውድ አባታቸው መታሰቢያ እንዲሆን ባሕር ዳር ውስጥ የከፈቱት “አባ መንገሻ ገነሜ የሕዝብ ቤተ መጻሕፍት እና የመረጃ ማዕከል” ነው።
ወጣቶች ትምህርታቸውን በትጋት እንዲቀጥሉ እና በሙሉ አቅማቸው ዓላማቸውን ለማሳካት እንዲጥሩ ለማበረታታት እና ለመደገፍ በምንም ዓይነት ወደኃላ አዩሉም ነበር።
በተለይም ለከፍተኛ ትምህርት እድሎችን ለማስፋት ከነበራቸው ጽኑ ፍላጎት በራሳቸው እና በባለቤታቸው ወይዘሮ ሕይወት ስም በሃርቫርድ ቢዝነስ ትምህርት ቤት የትምህርት ብቃት ላላቸው የአፍሪቃውያን ተማሪዎች ስኮላርሺፕ አቋቀቁመው ብዙ ተማሪዋች ሊጠቅሙ ችለዎል።
በፍቅር ወንድዬ ተብለው የሚጠሩትን ልጅ የወንድወሰን መንገሻን የማወቅ ዕድል ያገኙ ሁሉ ተንከባካቢነታቸውን፣ ትሁትነታቸውን እና ለጋሥነታቸውን ይመሰክራሉ። ዘመዶችን፣ ጓደኞችን እንዲሁም ሌሎች ሰዎች መርዳት እና ምክር በመለገስ ረገድ የተቻላቸውን ሁሉ አድርገዋል። እንዲሁም ታዳጊ እና ወጣት የሆኑት ዘመዶቻቸው እንደአባት እና አማካሪ ያዩዋቸው ነበር።
የቤተሰብ አባላት ታማኝነታቸውን እና ጥበባዊ ምክራቸውን ከፍ አድርገው ይመለከቷቸው ነበር። በተለይም የቅርብ ዘመዶቻቸው ከሆኑት ከራሥ አንዳርጋቸው መሳይ እና ከልዕልት ተናኘወርቅ ኃይለ ሥላሴ ፍቅር እና አክብሮት ምንግዜም አልተላያቸውም።
ልጅ የወንድወሰን እ ኤ አ ጥቅምት 12 ቀን 2025 በሎንዶን በሚገኘው ቤታቸው በቤተሰብ ተከበው በሰላም በማረፍ ከዚህ ዓለም ተለይተዋል።
በነሐሴ 23 ቀን 1964 ዓም እኤአ በትዳር ካገቧቸው ከውድ ባለቤታቸው ከወ/ሮ ሕይወት ግሬታ መንገሻ ጋር በፍቅር፣ በመከባበር እና በተድላ የዕድሜ ባለፀጋ ሆነው ያሬድ፣ ያድዋ እና የአደይን አፍርተዋል።
የሰባት የልጅ ልጆች አያት ለመሆን በቅተዋል - ካሌብ፣ ሶፊያ፣ ሉላዴይ (ሊሊ)፣ ጌሊላ፣ አሸር፣ ፀጋ እና ኢያሱ ። ቤተሰቡ መሪ አባት የነበሩትን በሞት በማጣታቸው በታላቅ ሀዘን ላይ ቢወድቁም አምላክ ረጅም ዕድሜ ስለሰጣቸው እና ቤተሰቡን ፍቅር በተሞላበት አርአያነት በመምራታቸው በምስጋና ተሞልተዋል።
እኚህ ትሁት የኢየሱስ ክርስቶስ አገልጋይ ፣ ቅዱስ ጳውሎስ በ1ኛ ቆሮንቶስ 13 ላይ እንዳስተማረው የፍቅር ምሳሌ ሆነው ኖረዋል።
“ፍቅር ታጋሽ ነው፣ ፍቅር ደግ ነው፣ ፍቅር አይመቀኝም፣ ፍቅር አይታበይም፣ ፍቅር አይኰራም፣
ፍቅር ስነስርዓተቢስ አይደለም፣ ፍቅር የራሱን ጥቅም ብቻ ፈላጊ አይደለም፣ ፍቅር አይበሳጭም፣ ፍቅር ቢበደልም እንኳ በደልን እንደበደል አይቆጥርም፣ ፍቅር እውነት በሆነ ነገር ይደሰታል እንጂ ክፋት በሆነ ነገር አይደሰትም፣ ፍቅር ሁሉን ችሎ ይታገሳል፣ ፍቅር በሁሉም ላይ ተስፋ የደርጋል፣ ፍቅር በሁሉም ነገር ይጸናል”
ቸሩ አምላክ ነፍሳቸውን የዘላለም እረፍት ይስጥልን።
Sponsored by
Surafel
10 months ago
አንቺ ቆንጆ ሴት ሲጋራ ማጨስን ማቆም አለብሽ !/ኤርዶጋን/
የቱርኩ ፕሬዝዳንት ሬሲፕ ጣይብ ኤርዶጋን የጣሊያን ጠቅላይ ሚኒስትር ሲጋራ ማጨስ እንድታቆም የቻለዉን እንደሚያደርግ መናገሩን ጆርጂያ ሜሎኒ ፖሊቲኮ ዘግቧል።
በግብፅ በጋዛ ያለውን ጦርነት ለማስቆም ከታቀደው የሰላም ጉባኤ ጎን ለጎን መገናኘታቸዉ የተገለፀ ሲሆን ኤርዶጋን ሜሎኒ "ማጨስን እንድታቆም የሚያሳምንበትን መንገድ እንደሚፈልግ ቃል ገብቷል።
በጣሊያን ዕለታዊ ኢል ፎሊዮ እና በሌሎች ሚዲያዎች እንደዘገቡት ከሆነ ኤርዶጋን ለሜሎኒ "በጣም ጥሩ ትመስያለሽ። ግን ማጨስ እንድታቆሚ ላደርግ ይገባል" ብሏል።
በተከታታይ ቃለ ምልልሶች ላይ በተመሰረተ መጽሐፍ ላይ ሜሎኒ ለ13 ዓመታት ካቆመች በኋላ እንደገና ማጨስ እንደጀመረች መናገሯን ተከትሎ ነዉ የኤርዶጋን አስተያየት የተሰጠው ።
በቱርክ በ1996 ዋና የትምባሆ ቁጥጥር ህግ የወጣ እና ብዙ ጊዜ የተሻሻለ ህግ ያላት ሲሆን ቁጥር 4207 በታሸጉ የህዝብ ቦታዎች እና የስራ ቦታዎች ማጨስን የሚከለክል፣ ከ18 አመት በታች ለሆኑ ታዳጊዎች የትምባሆ መሸጥን የሚከለክል እና ማስታወቂያ፣ የማስተዋወቅ ማሸግያቸዉን ሳቢ ማድረግ የሚገድብ ደንቦችን ያካተተ ህግ ነው።
ህጉ ለሲጋራ ማጨስ ተጋላጭነትን በመቀነስ እና ትንባሆ መጠቀምን በተለያዩ እርምጃዎች እና የማስፈጸሚያ እርምጃዎች በመቀነስ የህዝብ ጤናን ለመጠበቅ ያለመ ነው።
ኤርዶጋን ይህን ባሉበት ወቅት አጠገባቸው የነበሩት የፈረንሳዩ ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን የኤርዶጋንን ተስፋ ለማጨናገፍ በሚመስል መልኩ "የማይቻል ነው!" በማለት እየሳቀ ቀልዷል።
በተያያዘ ዜና የጣሊያን ጠቅላይ ሚኒስትር ሜሎኒ በመካከለኛው ምስራቅ የሰላም እቅድ ፊርማ ሥነ-ሥርዓት ላይ ለመገኘት በግብፅ በነበራቸው ቆይታ ከግብፁ ፕሬዝዳንት አብዱልፈታህ አል ሲሲ ጋር የሁለትዮሽ ውይይት አድርገዋል።
በኤክስ ላይ ባስተላለፈችው ጽሁፍ፣ 'የመካከለኛው ምስራቅ የሰላም እቅድ ከተፈራረመበት ስነ ስርዓት ጎን ለጎን ከግብፁ ፕሬዝዳንት አብደል ፈታህ አል ሲሲ ጋር የሁለትዮሽ ውይይት አድርጌያለሁ። የሰላም ዕቅዱን ተግባራዊ ለማድረግ በሚቀጥሉት እርምጃዎች ላይ ተወያይተናል እና ጣሊያን ለጋዛ ሰርጥ ማረጋጋት ፣ መልሶ ግንባታ እና ልማት የበኩሏን አስተዋጽኦ ለማበርከት እና በመካከለኛው ምስራቅ የሰላም ፣ የፀጥታ እና የመረጋጋት ማዕቀፍ ላይ የፖለቲካ ሂደትን ለማስጀመር በሁለቱ መንግስታት መፍትሄ ላይ በመመስረት ቁርጠኝነትን አረጋግጣለሁ።ብለዋል ።
የኔታ ቲዩብ ዘጋቢ ፦ ታዴ የማመይ ልጅ
የቱርኩ ፕሬዝዳንት ሬሲፕ ጣይብ ኤርዶጋን የጣሊያን ጠቅላይ ሚኒስትር ሲጋራ ማጨስ እንድታቆም የቻለዉን እንደሚያደርግ መናገሩን ጆርጂያ ሜሎኒ ፖሊቲኮ ዘግቧል።
በግብፅ በጋዛ ያለውን ጦርነት ለማስቆም ከታቀደው የሰላም ጉባኤ ጎን ለጎን መገናኘታቸዉ የተገለፀ ሲሆን ኤርዶጋን ሜሎኒ "ማጨስን እንድታቆም የሚያሳምንበትን መንገድ እንደሚፈልግ ቃል ገብቷል።
በጣሊያን ዕለታዊ ኢል ፎሊዮ እና በሌሎች ሚዲያዎች እንደዘገቡት ከሆነ ኤርዶጋን ለሜሎኒ "በጣም ጥሩ ትመስያለሽ። ግን ማጨስ እንድታቆሚ ላደርግ ይገባል" ብሏል።
በተከታታይ ቃለ ምልልሶች ላይ በተመሰረተ መጽሐፍ ላይ ሜሎኒ ለ13 ዓመታት ካቆመች በኋላ እንደገና ማጨስ እንደጀመረች መናገሯን ተከትሎ ነዉ የኤርዶጋን አስተያየት የተሰጠው ።
በቱርክ በ1996 ዋና የትምባሆ ቁጥጥር ህግ የወጣ እና ብዙ ጊዜ የተሻሻለ ህግ ያላት ሲሆን ቁጥር 4207 በታሸጉ የህዝብ ቦታዎች እና የስራ ቦታዎች ማጨስን የሚከለክል፣ ከ18 አመት በታች ለሆኑ ታዳጊዎች የትምባሆ መሸጥን የሚከለክል እና ማስታወቂያ፣ የማስተዋወቅ ማሸግያቸዉን ሳቢ ማድረግ የሚገድብ ደንቦችን ያካተተ ህግ ነው።
ህጉ ለሲጋራ ማጨስ ተጋላጭነትን በመቀነስ እና ትንባሆ መጠቀምን በተለያዩ እርምጃዎች እና የማስፈጸሚያ እርምጃዎች በመቀነስ የህዝብ ጤናን ለመጠበቅ ያለመ ነው።
ኤርዶጋን ይህን ባሉበት ወቅት አጠገባቸው የነበሩት የፈረንሳዩ ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን የኤርዶጋንን ተስፋ ለማጨናገፍ በሚመስል መልኩ "የማይቻል ነው!" በማለት እየሳቀ ቀልዷል።
በተያያዘ ዜና የጣሊያን ጠቅላይ ሚኒስትር ሜሎኒ በመካከለኛው ምስራቅ የሰላም እቅድ ፊርማ ሥነ-ሥርዓት ላይ ለመገኘት በግብፅ በነበራቸው ቆይታ ከግብፁ ፕሬዝዳንት አብዱልፈታህ አል ሲሲ ጋር የሁለትዮሽ ውይይት አድርገዋል።
በኤክስ ላይ ባስተላለፈችው ጽሁፍ፣ 'የመካከለኛው ምስራቅ የሰላም እቅድ ከተፈራረመበት ስነ ስርዓት ጎን ለጎን ከግብፁ ፕሬዝዳንት አብደል ፈታህ አል ሲሲ ጋር የሁለትዮሽ ውይይት አድርጌያለሁ። የሰላም ዕቅዱን ተግባራዊ ለማድረግ በሚቀጥሉት እርምጃዎች ላይ ተወያይተናል እና ጣሊያን ለጋዛ ሰርጥ ማረጋጋት ፣ መልሶ ግንባታ እና ልማት የበኩሏን አስተዋጽኦ ለማበርከት እና በመካከለኛው ምስራቅ የሰላም ፣ የፀጥታ እና የመረጋጋት ማዕቀፍ ላይ የፖለቲካ ሂደትን ለማስጀመር በሁለቱ መንግስታት መፍትሄ ላይ በመመስረት ቁርጠኝነትን አረጋግጣለሁ።ብለዋል ።
የኔታ ቲዩብ ዘጋቢ ፦ ታዴ የማመይ ልጅ
10 months ago
በኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ላይ የጥላቻ ንግግር በግል የማኅበራዊ ገጽ ላይ ሲለጥፍ የቆየው ግለሰብ በእስር ተቀጣ
#ethiopia | የኢሉ አባ ቦር ዞን፣ ሁሩሙ ወረዳ ፍርድ ቤት በግል የማኅበራዊ ሚዲያ ገጾቹ ላይ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሃይማኖትን በሚመለከት የጥላቻ ንግግር እና የሐሰት መረጃዎችን ሲያሰራጭ በነበረ ግለሰብ ላይ የ 1 ዓመት ከ 6 ወር እስራት ወስኗል ።
የተከሳሹ የማኅበራዊ ሚዲያ ጥፋት ዝርዝር እንደሚከተለው ቀርቧል
ተከሳሹ ተስፋሚካኤል ወንድምሙ ተኪሌ የተባለ ሲሆን፣ በሁሩሙ ወረዳ 01 ቀበሌ ነዋሪ ነው።
ተከሳሹ ከሰኔ 2017 ዓ.ም. ጀምሮ እስከ መስከረም 2018 ዓ.ም. ድረስ ባሉት ወራት “ዲያቆን ተስፋሚኬል ዘ-ክርስቶስ” እና “Tesfu Js” በተሰኙ የፌስቡክ የግል ገጾቹ ላይ የተለያዩ የጥላቻ ድርጊቶችን እና ጽሑፎችን ሲያሰራጭ መቆየቱ በፍርድ ቤት ተረጋግጧል።
ከእነዚህም መካከል፦
1. በእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ሥዕል ላይ የ'x' ምልክት ማድረግ።
2. የቅዱስ ክርስቶስ ሠምራ ሥዕል ላይ የውሻ ምስል አያይዞ “አቡነ ቡቼ” የሚል ጽሁፍ መለጠፍ።
3. በቪዲዮ ቀረጻ የእመቤታችንን ሥዕል መጣል።
* ስለ አቡነ ተክለ ሃይማኖት እና አቡነ አልባቲ ተክሌ የሚሉ ቃላትን በመጠቀም ጽሑፎችን መጻፍ እና መለጠፍ።
4. "ኦርቶዶክስ ካልታደሰች እጣ ፈንታዋ ሙዚየም መሆን ነው” የሚል መልዕክት ማሰራጨት።
5. 44ቱን አምላክ አመለካለሁ ራሴን ክርስቲያን እላለሁ” የሚል መረጃ መለጠፍ።
6. ታቦተ ጽዮን "ሽንት ቤት (የሽንት ቤት ፎጣ)" በሚል አግባብ የሌለው ጽሑፍ ማሰራጨት።
የህግ ተጠያቂነት እና ውሳኔ
በወረዳው የጸጥታ አካላት ክትትልና ቁጥጥር ስር የዋለው ተከሳሹ፣ በፖሊስና በዐቃቤ ህግ የጋራ ምርመራ ተደርጎበታል።
ዐቃቤ ህግ ያቀረበው ክስም ተከሳሹ ድርጊቱን የፈጸመው በወቅቱ በሥራ ላይ በነበረው በ1996 የወጣው የወንጀል ህግ አንቀጽ 32(1)(A) እና አዋጅ ቁጥር 1185/2012 አንቀጽ 4 እና 7 (1) ስር የተመለከቱትን የጥላቻ ንግግር እና የሃሰተኛ መረጃ ስርጭት መከልከል የሚመለከቱ ድንጋጌዎችን በመተላለፍ መሆኑን አስረድቷል።
በዚህም መሰረት በሁሩሙ ወረዳ ፍርድ ቤት በቀረበው ክስ፣ ችሎቱ የተከሳሹን የማህበራዊ ሚዲያ ላይ የተፈጸሙ የጥላቻ ድርጊቶችን እና የሃይማኖት ስሞችን ማጥላላት መፈጸሙን ካረጋገጠ በኋላ፣ 1 ዓመት ከ6 ወር ጽኑ እስራት እንዲቀጣ ወሳኔ አሳልፏል።
©️ሁሩሙ ወረዳ ኮሚኒኬሽን ቢሮ
#ethiopia | የኢሉ አባ ቦር ዞን፣ ሁሩሙ ወረዳ ፍርድ ቤት በግል የማኅበራዊ ሚዲያ ገጾቹ ላይ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሃይማኖትን በሚመለከት የጥላቻ ንግግር እና የሐሰት መረጃዎችን ሲያሰራጭ በነበረ ግለሰብ ላይ የ 1 ዓመት ከ 6 ወር እስራት ወስኗል ።
የተከሳሹ የማኅበራዊ ሚዲያ ጥፋት ዝርዝር እንደሚከተለው ቀርቧል
ተከሳሹ ተስፋሚካኤል ወንድምሙ ተኪሌ የተባለ ሲሆን፣ በሁሩሙ ወረዳ 01 ቀበሌ ነዋሪ ነው።
ተከሳሹ ከሰኔ 2017 ዓ.ም. ጀምሮ እስከ መስከረም 2018 ዓ.ም. ድረስ ባሉት ወራት “ዲያቆን ተስፋሚኬል ዘ-ክርስቶስ” እና “Tesfu Js” በተሰኙ የፌስቡክ የግል ገጾቹ ላይ የተለያዩ የጥላቻ ድርጊቶችን እና ጽሑፎችን ሲያሰራጭ መቆየቱ በፍርድ ቤት ተረጋግጧል።
ከእነዚህም መካከል፦
1. በእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ሥዕል ላይ የ'x' ምልክት ማድረግ።
2. የቅዱስ ክርስቶስ ሠምራ ሥዕል ላይ የውሻ ምስል አያይዞ “አቡነ ቡቼ” የሚል ጽሁፍ መለጠፍ።
3. በቪዲዮ ቀረጻ የእመቤታችንን ሥዕል መጣል።
* ስለ አቡነ ተክለ ሃይማኖት እና አቡነ አልባቲ ተክሌ የሚሉ ቃላትን በመጠቀም ጽሑፎችን መጻፍ እና መለጠፍ።
4. "ኦርቶዶክስ ካልታደሰች እጣ ፈንታዋ ሙዚየም መሆን ነው” የሚል መልዕክት ማሰራጨት።
5. 44ቱን አምላክ አመለካለሁ ራሴን ክርስቲያን እላለሁ” የሚል መረጃ መለጠፍ።
6. ታቦተ ጽዮን "ሽንት ቤት (የሽንት ቤት ፎጣ)" በሚል አግባብ የሌለው ጽሑፍ ማሰራጨት።
የህግ ተጠያቂነት እና ውሳኔ
በወረዳው የጸጥታ አካላት ክትትልና ቁጥጥር ስር የዋለው ተከሳሹ፣ በፖሊስና በዐቃቤ ህግ የጋራ ምርመራ ተደርጎበታል።
ዐቃቤ ህግ ያቀረበው ክስም ተከሳሹ ድርጊቱን የፈጸመው በወቅቱ በሥራ ላይ በነበረው በ1996 የወጣው የወንጀል ህግ አንቀጽ 32(1)(A) እና አዋጅ ቁጥር 1185/2012 አንቀጽ 4 እና 7 (1) ስር የተመለከቱትን የጥላቻ ንግግር እና የሃሰተኛ መረጃ ስርጭት መከልከል የሚመለከቱ ድንጋጌዎችን በመተላለፍ መሆኑን አስረድቷል።
በዚህም መሰረት በሁሩሙ ወረዳ ፍርድ ቤት በቀረበው ክስ፣ ችሎቱ የተከሳሹን የማህበራዊ ሚዲያ ላይ የተፈጸሙ የጥላቻ ድርጊቶችን እና የሃይማኖት ስሞችን ማጥላላት መፈጸሙን ካረጋገጠ በኋላ፣ 1 ዓመት ከ6 ወር ጽኑ እስራት እንዲቀጣ ወሳኔ አሳልፏል።
©️ሁሩሙ ወረዳ ኮሚኒኬሽን ቢሮ
11 months ago
በኢትዮጵያ ዘመናዊ ውትድርና ታሪክ አንድ የታሪክ ምዕራፍ ተዘጋ
ከአለባቸው ደሳለኝ አበሻ (ለንደን)
#ethiopia | ዶ/ር ሜ/ጄኔራ መስፍን ገብረ ቃል የኢትዮጵያ መለያ ምልክት August 1937 ተወለዱ August
2025 በተወለዱ 88 አመታቸው ከዚህ አለም በሞት ተለየ ።
August 28 /2025 በእንግሊዝ ሐገር በለንደን ከተማ
የቀብር ስነስርአታቸው ተፈፀመ።
ዶ/ር ሜ/ጄኔራ መስፍን ገብረ ቃል
በኖሩባቸው በእነዚህ አመታቶች ውስጥ ከባለቤታቸው ከወ/ሮ ሙሉ ተ/ብርሀን አራት ልጆችን አፍርተዋል
የትምሕርት ዝግጅታቸውን በተመለከተ ፤
*በ1958 ዓ/ም በቀዳማዊ ሐይለስላሴ ዘመነ መንግስት ከተመረጡት ሁለት ተማሪወች አንዱ በመሆን እንግሊዝ አገር ከሳናደርስት ሮያል ወታደራዊ አካዳሚ ከፍተኛ ወታደራዊ ትምህርት ተምረው ተመርቀዋል ።
*በ1668 አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ በሕግ ዲግሪ ተመርቀዋል።
*በ1969 Camberley British Army staff College (P.S.C)
*በ1996 ከኪንግስ ኮለጅ ለንደን የጦርነት ጥናቶች ክፍል የማስተር ዲግሪ (MA)department of War studies
*2002 ፒኤችዲ (PHD) የአፍሪካ ቀንድ : ከቀዝቃዛው ጦርነት በሗላ የደህንነት ተለዋዋጭ ባህሪ (the horn of africa challenging nature off security in the aftermath of the cold War) ዲግሪያቸው ተቀብለዋል ።
ዶ/ር ሜ/ጄኔራ መስፍን ገብረ ቃል በህይወት ዘመናቸዉ ከተለያዩ ከፍተኛ የመንግስት ተቋማት ልዩ ልዩ ሽልማቶችን ተቀብለዋል ።
* ከተባበሩት መንግስታት የአገልግሎት ሜዳሊያ ።
(UN service medal)
ኮንጎ የሠላም ሜዳል
(Congo peace medal)
የሁለት ናይሎች ትዕዛዝ በሡዳኑ ፕሬዝዳንት ኑሜሪ ተሸልመዋል
(Order of the two Nile by president numeri of the Sudan )
* ከ1977- 1978 በኢትዮጵያና በአጎራባቿ ሡማሊያ በተደረገው ከፍተኛ ጦርነት በሠጡት ወታደራዊ አመራር የኢትዮጵያ አንደኛ ደረጃ የጀግና ሜዳይ ተሸላሚ ነበሩ ።
ዶ/ር ሜ/ጄኔራ መስፍን ገብረ ቃል
በኢትዮጵያ ውስጥ ብቻ ሳይሆን በተባበሩት መንግስታት የሠላም አስከባሪ በመሆን ለአደረጉት አስተዋፅዎ ከፍተኛ ምስጋናን ተቀብለዋል ።
ዶ/ር ሜ/ጄኔራ መስፍን ገብረ ቃል
ብዙ አስቸጋሪ የህይወት ውጣ ውረድ በሚታይበት ወታደራዊ ሞያ ሙሉ ሕይወታቸውን ለኢትዮጵያ አገራቸው ሰተው አልፈዋል ::
ዶ/ር ሜ/ጄኔራ መስፍን ገብረ ቃል
በጥይት እርሳስ እየተቆሉ በቦንብ ውርጅብኝ መላ አካላታቸው እየነደደ ላንቃቸው እሳት በሚተፉ ከባድና ቀላል መሳሪያዎች በግንባርና በደረታቸው በእግርና በእጃቸው በመላ አካላታቸው ላይ ጥይቶች እያራገፉባቸው ደማቸውን አፍስሰው ህይወታቸውን ከገብሩት የቀድሞ የኢትዮጵያ ሰራዊት ጎን ተሠልፈው ለኢትዮጵያ አንድነት ከታገሉት ከፍተኛ የጦር አዛዦች አንዱ ነበሩ።
ዶ/ር ሜ/ጄኔራ መስፍን ገብረ ቃል
የሶስት ሽህ ዘመን የታሪክ አውራ የሆነች ታላቅ ሐገራቸው ኢትዮጰያ ህልውናዋን፣ ማስቀጠል ደንበሯን መጠበቅ የታሪክ ሀላፊነት በሳቸውና በጓዶቻቸው እጅ ሲወድቅ
ግንቦት 19 ቀን 1983 ከቀድሞ የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ተስፋዬ ዲንቃ ጋር በመሆን ከሻዕቢያ፣ እንዲሁም ከወያኔና ከኦሮሞ ነጻነት ግንባር ጋር ሊካሄድ በታቀደው ድርድር ለመሳተፍ የመንግስት ልዑካን ከነበሩት አንዱ በመሆን ለድርድር እንግሊዝ አገር ለንደን ገቡ ።
በአሜሪካን መንግስት የተመራው የሽምግልና ድርድር ኤርትራን አስገንጥሎ ወያኔን ኢትዮጵያ ላይ አንግሶ በአሳዛኝ ሁኔታ ያለ ውጤት ተደመደመ ።
ዶ/ር ሜ/ጄኔራ መስፍን ገብረ ቃል ወደሐገራቸው ሳይመለሡ
ህይወታቸው እሰከአለፈበት ነሐሴ 11/2025 ድረስ ከ30 አመት በላይ በስደት እንግሊዝ አገር ኑረዋል።
በመጨረሻ ግን ሕይወታቸው ካለፈ በሗላ በቤተሠቦቻቸው ምርጫ ለክብሯ ቆመው በነፍስ በሥጋ በአጥንት በደም ታላቅን የማይተካ ክቡር መስዋዕትነት፣ ታላቅን ውድ ሕይወታቸውን ከፍለው ኢትዮጵያ እድተቀጥል ያደረጉት ጀግና
ዶ/ር ሜ/ጄኔራ መስፍን ገብረ ቃል
የኸደፊቱን መገመት ባልችልም
በባዕድ አገር አስከሬናቸው ሲቀር እንደዜጋ ልቤ ተሰብሮ አልቅሻለሁ ።
የኢትዮጵያ ጀግኖች አደራ ውስጡ ድረስ ዘልቆ የሚሰማው የትኛውም ባለአደራ ትውልድ፣ እንደ ዶ/ር
ሜ/ጄኔራ መስፍን ገብረ ቃል የመሳሰሉ ጀግኖች ለኢትዮጵያ አንድነት የከፈሉለትን የነፃነት ዋጋ
ታሳቢ በማድረግ አፅማቸው በትውልድ ሐገራቸው እንዲያርፍ የማድረግ ትልቅ ሐላፊነት አለበት ብየ አምናለሁ ።
ወዳጆቼ !!
ከተሳካልኝ ወደፊት ቤተሠቦቻቸውን አነጋግሬ በሠፊው እመለስበታለሁ ።
እስከዚያው ቸር ያቆየን ።
ከአለባቸው ደሳለኝ አበሻ (ለንደን)
#ethiopia | ዶ/ር ሜ/ጄኔራ መስፍን ገብረ ቃል የኢትዮጵያ መለያ ምልክት August 1937 ተወለዱ August
2025 በተወለዱ 88 አመታቸው ከዚህ አለም በሞት ተለየ ።
August 28 /2025 በእንግሊዝ ሐገር በለንደን ከተማ
የቀብር ስነስርአታቸው ተፈፀመ።
ዶ/ር ሜ/ጄኔራ መስፍን ገብረ ቃል
በኖሩባቸው በእነዚህ አመታቶች ውስጥ ከባለቤታቸው ከወ/ሮ ሙሉ ተ/ብርሀን አራት ልጆችን አፍርተዋል
የትምሕርት ዝግጅታቸውን በተመለከተ ፤
*በ1958 ዓ/ም በቀዳማዊ ሐይለስላሴ ዘመነ መንግስት ከተመረጡት ሁለት ተማሪወች አንዱ በመሆን እንግሊዝ አገር ከሳናደርስት ሮያል ወታደራዊ አካዳሚ ከፍተኛ ወታደራዊ ትምህርት ተምረው ተመርቀዋል ።
*በ1668 አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ በሕግ ዲግሪ ተመርቀዋል።
*በ1969 Camberley British Army staff College (P.S.C)
*በ1996 ከኪንግስ ኮለጅ ለንደን የጦርነት ጥናቶች ክፍል የማስተር ዲግሪ (MA)department of War studies
*2002 ፒኤችዲ (PHD) የአፍሪካ ቀንድ : ከቀዝቃዛው ጦርነት በሗላ የደህንነት ተለዋዋጭ ባህሪ (the horn of africa challenging nature off security in the aftermath of the cold War) ዲግሪያቸው ተቀብለዋል ።
ዶ/ር ሜ/ጄኔራ መስፍን ገብረ ቃል በህይወት ዘመናቸዉ ከተለያዩ ከፍተኛ የመንግስት ተቋማት ልዩ ልዩ ሽልማቶችን ተቀብለዋል ።
* ከተባበሩት መንግስታት የአገልግሎት ሜዳሊያ ።
(UN service medal)
ኮንጎ የሠላም ሜዳል
(Congo peace medal)
የሁለት ናይሎች ትዕዛዝ በሡዳኑ ፕሬዝዳንት ኑሜሪ ተሸልመዋል
(Order of the two Nile by president numeri of the Sudan )
* ከ1977- 1978 በኢትዮጵያና በአጎራባቿ ሡማሊያ በተደረገው ከፍተኛ ጦርነት በሠጡት ወታደራዊ አመራር የኢትዮጵያ አንደኛ ደረጃ የጀግና ሜዳይ ተሸላሚ ነበሩ ።
ዶ/ር ሜ/ጄኔራ መስፍን ገብረ ቃል
በኢትዮጵያ ውስጥ ብቻ ሳይሆን በተባበሩት መንግስታት የሠላም አስከባሪ በመሆን ለአደረጉት አስተዋፅዎ ከፍተኛ ምስጋናን ተቀብለዋል ።
ዶ/ር ሜ/ጄኔራ መስፍን ገብረ ቃል
ብዙ አስቸጋሪ የህይወት ውጣ ውረድ በሚታይበት ወታደራዊ ሞያ ሙሉ ሕይወታቸውን ለኢትዮጵያ አገራቸው ሰተው አልፈዋል ::
ዶ/ር ሜ/ጄኔራ መስፍን ገብረ ቃል
በጥይት እርሳስ እየተቆሉ በቦንብ ውርጅብኝ መላ አካላታቸው እየነደደ ላንቃቸው እሳት በሚተፉ ከባድና ቀላል መሳሪያዎች በግንባርና በደረታቸው በእግርና በእጃቸው በመላ አካላታቸው ላይ ጥይቶች እያራገፉባቸው ደማቸውን አፍስሰው ህይወታቸውን ከገብሩት የቀድሞ የኢትዮጵያ ሰራዊት ጎን ተሠልፈው ለኢትዮጵያ አንድነት ከታገሉት ከፍተኛ የጦር አዛዦች አንዱ ነበሩ።
ዶ/ር ሜ/ጄኔራ መስፍን ገብረ ቃል
የሶስት ሽህ ዘመን የታሪክ አውራ የሆነች ታላቅ ሐገራቸው ኢትዮጰያ ህልውናዋን፣ ማስቀጠል ደንበሯን መጠበቅ የታሪክ ሀላፊነት በሳቸውና በጓዶቻቸው እጅ ሲወድቅ
ግንቦት 19 ቀን 1983 ከቀድሞ የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ተስፋዬ ዲንቃ ጋር በመሆን ከሻዕቢያ፣ እንዲሁም ከወያኔና ከኦሮሞ ነጻነት ግንባር ጋር ሊካሄድ በታቀደው ድርድር ለመሳተፍ የመንግስት ልዑካን ከነበሩት አንዱ በመሆን ለድርድር እንግሊዝ አገር ለንደን ገቡ ።
በአሜሪካን መንግስት የተመራው የሽምግልና ድርድር ኤርትራን አስገንጥሎ ወያኔን ኢትዮጵያ ላይ አንግሶ በአሳዛኝ ሁኔታ ያለ ውጤት ተደመደመ ።
ዶ/ር ሜ/ጄኔራ መስፍን ገብረ ቃል ወደሐገራቸው ሳይመለሡ
ህይወታቸው እሰከአለፈበት ነሐሴ 11/2025 ድረስ ከ30 አመት በላይ በስደት እንግሊዝ አገር ኑረዋል።
በመጨረሻ ግን ሕይወታቸው ካለፈ በሗላ በቤተሠቦቻቸው ምርጫ ለክብሯ ቆመው በነፍስ በሥጋ በአጥንት በደም ታላቅን የማይተካ ክቡር መስዋዕትነት፣ ታላቅን ውድ ሕይወታቸውን ከፍለው ኢትዮጵያ እድተቀጥል ያደረጉት ጀግና
ዶ/ር ሜ/ጄኔራ መስፍን ገብረ ቃል
የኸደፊቱን መገመት ባልችልም
በባዕድ አገር አስከሬናቸው ሲቀር እንደዜጋ ልቤ ተሰብሮ አልቅሻለሁ ።
የኢትዮጵያ ጀግኖች አደራ ውስጡ ድረስ ዘልቆ የሚሰማው የትኛውም ባለአደራ ትውልድ፣ እንደ ዶ/ር
ሜ/ጄኔራ መስፍን ገብረ ቃል የመሳሰሉ ጀግኖች ለኢትዮጵያ አንድነት የከፈሉለትን የነፃነት ዋጋ
ታሳቢ በማድረግ አፅማቸው በትውልድ ሐገራቸው እንዲያርፍ የማድረግ ትልቅ ሐላፊነት አለበት ብየ አምናለሁ ።
ወዳጆቼ !!
ከተሳካልኝ ወደፊት ቤተሠቦቻቸውን አነጋግሬ በሠፊው እመለስበታለሁ ።
እስከዚያው ቸር ያቆየን ።
12 months ago
በአረካ ከተማ የሆቴል ቤት አስተናጋጅን በቢላ ወግቶ የገደለው የሆቴሉ ማናጀር በእስራት ተቀጣ
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በወላይታ ዞን በአረካ ከተማ አስተዳደር ሰፈረ ሰላም ቀበሌ ሩፋኤል ሆቴል ሚያዚያ 11 ቀን 2017 በግምት ከቀኑ 11፡00 ሰዓት በሚሆንበት ጊዜ ነው የወንጀል ድርጊቱ የተፈፀመው ።
ተከሳሽ የሆነው ግለሰብ ታደሌ ክፍሌ የተባለ ሲሆን ማናጄር ሆኖ የሚሰራበት ሩፋኤል ሆቴል ላይ መስትንግዶ ከምትሰራው ሙሉ አለሙ የተባለችውን ጋር በመጋጨቱ ምክንያት በአሰቃቂ ሁኔታ በቢላዋ ወግቶ ህይወቷ እንዲያልፍ ካደረገ በኋላ ለማምለጥ ሲሞክር በቁጥጥር ስር መዋሉን የደቡብ ኢትዮጵያ ፖሊስ ኮሚሽን ህዝብ ግንኙነት እና ገጽታ ግንባታ ዳይሬክተር ምክትል ኮማንደር አሸናፊ ኃይሌ ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል።
ይህ መረጃ የደረሰው የአረካ ከተማ ፖሊስ ተጠርጣሪውን በቁጥጥር ስር አውሎ የሟችን አስክሬን ለምርመራ ወደ ዱቦ ሆስፒታል በመላክ ለተፈፀመው ድርጊት አስፈለጊ የሆኑ የሰውና የሰነድ ማስረጃዎች አሰባስቦ ምርመራ በማጣራት መዝገብ አደራጅቶ ለወላይታ ዞን ዓ/ህግ ይቀርባል።
አቃቢ ህግም ከፖሊስ የቀረበለትን የምርመራ መዝገብ አይቶና ፈትሾ ተከሳሹ በ1996 ዓ.ም የወጣውን የኤ.ፌ.ድ.ሪ. የወንጀል ህግ አንቀጽ 539(1)(ሀ) ስር የተደነገገውን በመተላለፍ በፈፀመው ከበድ የሰው ግድያ ወንጀል ክስ መስርቶ ለወላይታ ዞን ከፍተኛ ፍ/ቤት ያቀርበዋል።
የወላይታ ዞን ከፍተኛ ፍ/ቤት ሐምሌ 28 ቀን 2017 ዓ.ም በዋለው የወንጀል ችሎት ተከሳሽን ያርማል ሌሎችን መሳል ድርጊት የሚፈፅሙ አካላትን ያስተምራል በማለት ተከሳሽ ታደሌ ክፍሌን በዕድሜ ልክ በፅኑ እስራት እንዲቀጣ ወስኖበታል ሲሉ ዳይሬክተር ምክትል ኮማንደር አሸናፊ ኃይሌ ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል።
በሳምራዊት ስዩም
#ዳጉ_ጆርናል
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በወላይታ ዞን በአረካ ከተማ አስተዳደር ሰፈረ ሰላም ቀበሌ ሩፋኤል ሆቴል ሚያዚያ 11 ቀን 2017 በግምት ከቀኑ 11፡00 ሰዓት በሚሆንበት ጊዜ ነው የወንጀል ድርጊቱ የተፈፀመው ።
ተከሳሽ የሆነው ግለሰብ ታደሌ ክፍሌ የተባለ ሲሆን ማናጄር ሆኖ የሚሰራበት ሩፋኤል ሆቴል ላይ መስትንግዶ ከምትሰራው ሙሉ አለሙ የተባለችውን ጋር በመጋጨቱ ምክንያት በአሰቃቂ ሁኔታ በቢላዋ ወግቶ ህይወቷ እንዲያልፍ ካደረገ በኋላ ለማምለጥ ሲሞክር በቁጥጥር ስር መዋሉን የደቡብ ኢትዮጵያ ፖሊስ ኮሚሽን ህዝብ ግንኙነት እና ገጽታ ግንባታ ዳይሬክተር ምክትል ኮማንደር አሸናፊ ኃይሌ ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል።
ይህ መረጃ የደረሰው የአረካ ከተማ ፖሊስ ተጠርጣሪውን በቁጥጥር ስር አውሎ የሟችን አስክሬን ለምርመራ ወደ ዱቦ ሆስፒታል በመላክ ለተፈፀመው ድርጊት አስፈለጊ የሆኑ የሰውና የሰነድ ማስረጃዎች አሰባስቦ ምርመራ በማጣራት መዝገብ አደራጅቶ ለወላይታ ዞን ዓ/ህግ ይቀርባል።
አቃቢ ህግም ከፖሊስ የቀረበለትን የምርመራ መዝገብ አይቶና ፈትሾ ተከሳሹ በ1996 ዓ.ም የወጣውን የኤ.ፌ.ድ.ሪ. የወንጀል ህግ አንቀጽ 539(1)(ሀ) ስር የተደነገገውን በመተላለፍ በፈፀመው ከበድ የሰው ግድያ ወንጀል ክስ መስርቶ ለወላይታ ዞን ከፍተኛ ፍ/ቤት ያቀርበዋል።
የወላይታ ዞን ከፍተኛ ፍ/ቤት ሐምሌ 28 ቀን 2017 ዓ.ም በዋለው የወንጀል ችሎት ተከሳሽን ያርማል ሌሎችን መሳል ድርጊት የሚፈፅሙ አካላትን ያስተምራል በማለት ተከሳሽ ታደሌ ክፍሌን በዕድሜ ልክ በፅኑ እስራት እንዲቀጣ ወስኖበታል ሲሉ ዳይሬክተር ምክትል ኮማንደር አሸናፊ ኃይሌ ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል።
በሳምራዊት ስዩም
#ዳጉ_ጆርናል
1 year ago
ከእንጦጦ ፓርክ የመብራት ገመዶችን የሰረቁ እስከ 23 ዓመት በሚደርስ እስራት ተቀጡ
የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 1ኛ ልዩ ልዩ የወንጀል ጉዳዮች ችሎት ከእንጦጦ ፓርክ የመብራት ገመዶችን በመቁረጥ የስርቆት ወንጀል የፈጸሙ ግለሰቦች እስከ 23 ዓመት በሚደርስ ጽኑ እስራት እንዲቀጡ ወሰነ።
ችሎቱ የግራ ቀኝ ማስረጃ መርምሮ ተከሳሾቹን በተደራራቢ ክሶች ጥፋተኛ በማለት በየመዝገብ ደረጃቸው በጽኑ እስራት እንዲቀጡ ወስኗል።
ተከሳሾቹ በአዲስ አበባ በተለያዩ ክፍለ ከተማዎች ነዋሪ የሆኑት መልካሙ ማቲዎስ፣ ቢኒያም ካሳሁን፣ ደረጄ ተሰማ፣ ቶፊቅ ዓለሙ፣ አማኑኤል አቡ፣ አስመላሽ ትግስቱ እና በሌለበት ጉዳዩ የታየው ዓለሙ ተመስገን ናቸው።
የፍትሕ ሚኒስቴር የጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ ዘርፍ የጉለሌ ቅርጫፍ ዐቃቤ ሕግ ተከሳሾቹ በ1996 ዓ.ም የወጣውን የወንጀል ሕግ አንቀጽ 32 ንዑስ ቁጥር (1) ሀ እና የቴሌ ኮሙኒኬሽን እና የኤሌክትሪክ ሀይል አውታሮችን ለመጠበቅ የወጣውን አዋጅ ቁጥር 464/97 አንቀጽ 4 ስር የተመለከተውን ድንጋጌ መተላለፋቸውን ጠቅሶ ተደራራቢ ዝርዝር ክስ አቅርቦባቸዋል።
በዚህም ተከሳሾቹ በየደረጃው በተለያዩ ጊዜ በሌሊት እንጦጦ ፓርክ ግቢ ውስጥ ንብረትነቱ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የህዝብ መዝናኛ ፓርኮች ኮርፖሬሽን የሆነ ለመብራት አገልግሎት እንዲውሉ የተዘረጉ የኤሌክትሪክ ገመዶችን በተለያዩ ቀናት እየቆረጡ በተሽከርካሪ በመጫን ሰርቀው በመውሰድ ሸጠው በመከፋፈል ተግባር ተሰማርተው እንደነበር በክሱ ተመላክቷል።
በጥቅምት 4 ቀን 2016 ዓ.ም ደግሞ በጉለሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 7 ልዩ ቦታው እንጦጦ ሲኒማ ላይ በ4ኛ ተከሳሽ መሪነት 5ኛ ተከሳሽ ደግሞ የኤሌክትሪክ ገመድ መቁረጫ የብረት መጋዝ በመያዝ 3ኛ ተከሳሽ በሚያሽከረክረው ኮድ1 ላዳ ተሽከርካሪ ለእንጦጦ ፓርክ አገልግሎት እንዲውል የተዘረጋ የኤሌክትሪክ ገመድ ቆርጠው ሊወስዱ ሲሉ በፀጥታ አካላት የተያዙ በመሆኑ በፈጸሙት በዋና ወንጀል አድራጊነት ተካፋይ በመሆን የኤሌክተሪክ አውታር ስርቆት ሙከራ ወንጀል ተከሰዋል።
ከተከሳሾቹ መካከል መልካሙ ማቲዎስ የተባለው ተከሳሽ 7 ተደራራቢ ክስ የቀረበበት ሲሆን÷ ቀሪዎቹ ደግሞ ከ2 እስከ 3 ተደራራቢ የክሶች ቀርቦባቸዋል።
ፍርድ ቤቱ ዐቃቤ ሕግ ያቀረበውን የሰውና የሰነድ ማስረጃ መርምሮ ተከሳሾቹ እንዲከላከሉ ብይን የሰጠ ሲሆን፤ ተከሳሾቹ የዐቃቤ ሕግ ማስረጃን በተገቢው ማስተባበል ባለመቻላቸው የጥፋተኝነት ፍርድ ተላልፎባቸዋል።
ከዚህም በኋላ ፍርድ ቤቱ የግራ ቀኝ የቅጣት አስተያየት መርምሮና ይዞ ወንጀሉ የተፈጸመው የሀገር ኃብት በሆነ መሰረተ ልማት ላይ በቡድንና በስምምነት፣ በሌሊት መሆኑን ማክበጃ በመያዝ 1ኛ ተከሳሽ መልካሙ ማቲዎስን ጥፋተኛ በተባለባቸው በ7 ክሶች ማለትም በእያንዳንዱ መዝገብ 3 እና 5 ዓመት ቅጣት በአጠቃላይ በድምሩ 23 ዓመት ጽኑ እስራት እንዲቀጣ ወስኗል።
ቀሪ ተከሳሾች ደግሞ በየደረጃው ጥፋተኛ በተባሉባቸው ተደራራቢ መዝገቦች በያንዳንዱ መዝገብ ሲደመር ከ9 እስከ 6 ዓመት በሚደርስ ጽኑ እስራት እንዲቀጡ ተወስኖባቸዋል።
FBC
የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 1ኛ ልዩ ልዩ የወንጀል ጉዳዮች ችሎት ከእንጦጦ ፓርክ የመብራት ገመዶችን በመቁረጥ የስርቆት ወንጀል የፈጸሙ ግለሰቦች እስከ 23 ዓመት በሚደርስ ጽኑ እስራት እንዲቀጡ ወሰነ።
ችሎቱ የግራ ቀኝ ማስረጃ መርምሮ ተከሳሾቹን በተደራራቢ ክሶች ጥፋተኛ በማለት በየመዝገብ ደረጃቸው በጽኑ እስራት እንዲቀጡ ወስኗል።
ተከሳሾቹ በአዲስ አበባ በተለያዩ ክፍለ ከተማዎች ነዋሪ የሆኑት መልካሙ ማቲዎስ፣ ቢኒያም ካሳሁን፣ ደረጄ ተሰማ፣ ቶፊቅ ዓለሙ፣ አማኑኤል አቡ፣ አስመላሽ ትግስቱ እና በሌለበት ጉዳዩ የታየው ዓለሙ ተመስገን ናቸው።
የፍትሕ ሚኒስቴር የጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ ዘርፍ የጉለሌ ቅርጫፍ ዐቃቤ ሕግ ተከሳሾቹ በ1996 ዓ.ም የወጣውን የወንጀል ሕግ አንቀጽ 32 ንዑስ ቁጥር (1) ሀ እና የቴሌ ኮሙኒኬሽን እና የኤሌክትሪክ ሀይል አውታሮችን ለመጠበቅ የወጣውን አዋጅ ቁጥር 464/97 አንቀጽ 4 ስር የተመለከተውን ድንጋጌ መተላለፋቸውን ጠቅሶ ተደራራቢ ዝርዝር ክስ አቅርቦባቸዋል።
በዚህም ተከሳሾቹ በየደረጃው በተለያዩ ጊዜ በሌሊት እንጦጦ ፓርክ ግቢ ውስጥ ንብረትነቱ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የህዝብ መዝናኛ ፓርኮች ኮርፖሬሽን የሆነ ለመብራት አገልግሎት እንዲውሉ የተዘረጉ የኤሌክትሪክ ገመዶችን በተለያዩ ቀናት እየቆረጡ በተሽከርካሪ በመጫን ሰርቀው በመውሰድ ሸጠው በመከፋፈል ተግባር ተሰማርተው እንደነበር በክሱ ተመላክቷል።
በጥቅምት 4 ቀን 2016 ዓ.ም ደግሞ በጉለሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 7 ልዩ ቦታው እንጦጦ ሲኒማ ላይ በ4ኛ ተከሳሽ መሪነት 5ኛ ተከሳሽ ደግሞ የኤሌክትሪክ ገመድ መቁረጫ የብረት መጋዝ በመያዝ 3ኛ ተከሳሽ በሚያሽከረክረው ኮድ1 ላዳ ተሽከርካሪ ለእንጦጦ ፓርክ አገልግሎት እንዲውል የተዘረጋ የኤሌክትሪክ ገመድ ቆርጠው ሊወስዱ ሲሉ በፀጥታ አካላት የተያዙ በመሆኑ በፈጸሙት በዋና ወንጀል አድራጊነት ተካፋይ በመሆን የኤሌክተሪክ አውታር ስርቆት ሙከራ ወንጀል ተከሰዋል።
ከተከሳሾቹ መካከል መልካሙ ማቲዎስ የተባለው ተከሳሽ 7 ተደራራቢ ክስ የቀረበበት ሲሆን÷ ቀሪዎቹ ደግሞ ከ2 እስከ 3 ተደራራቢ የክሶች ቀርቦባቸዋል።
ፍርድ ቤቱ ዐቃቤ ሕግ ያቀረበውን የሰውና የሰነድ ማስረጃ መርምሮ ተከሳሾቹ እንዲከላከሉ ብይን የሰጠ ሲሆን፤ ተከሳሾቹ የዐቃቤ ሕግ ማስረጃን በተገቢው ማስተባበል ባለመቻላቸው የጥፋተኝነት ፍርድ ተላልፎባቸዋል።
ከዚህም በኋላ ፍርድ ቤቱ የግራ ቀኝ የቅጣት አስተያየት መርምሮና ይዞ ወንጀሉ የተፈጸመው የሀገር ኃብት በሆነ መሰረተ ልማት ላይ በቡድንና በስምምነት፣ በሌሊት መሆኑን ማክበጃ በመያዝ 1ኛ ተከሳሽ መልካሙ ማቲዎስን ጥፋተኛ በተባለባቸው በ7 ክሶች ማለትም በእያንዳንዱ መዝገብ 3 እና 5 ዓመት ቅጣት በአጠቃላይ በድምሩ 23 ዓመት ጽኑ እስራት እንዲቀጣ ወስኗል።
ቀሪ ተከሳሾች ደግሞ በየደረጃው ጥፋተኛ በተባሉባቸው ተደራራቢ መዝገቦች በያንዳንዱ መዝገብ ሲደመር ከ9 እስከ 6 ዓመት በሚደርስ ጽኑ እስራት እንዲቀጡ ተወስኖባቸዋል።
FBC
1 year ago
በሞባይል ባንኪንግ ማጭበርበር ወንጀል በተጠረጠሩ 80 ግለሰቦች ላይ ክስ ተመሰረተ
#ethiopia | በሞባይል ባንኪንግ ማጭበርበር ወንጀል በተጠረጠሩ 80 ግለሰቦች ላይ የፌደራል ዐቃቤ ሕግ ክስ እንደመሰረተ የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ተገልጿል።
ይህ የተገለጸው የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ የ2016/2017 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈፃፀምን ከተለያዩ የዘርፉ ተጠሪዎች ጋር እየገመገመ ባለበት መድረክ ላይ ነው።
የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ የወንጀል ምርመራ ጠቅላይ መምሪያ ተወካይ አቶ ሙሊሳ አብዲሳ ባቀረቡት ሪፖርት፣ በሞባይል ባንኪንግ አማካኝነት ከ116 ግለሰቦች ላይ ከ30 ሚሊዮን ብር በላይ በሞባይል ባንኪግ በማጭበርበር ወንጀል በተጠረጠሩ 80 ግለሰቦች ላይ የፌደራል ዐቃቤ ሕግ ክስ እንደተመሰረተባቸውገልጸዋል።
ተከሳሾቹ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ከሌሎች የግል ባንኮች የሚደውሉ በማስመሰል እንዲሁም የኮምፒውተር ሥርዓትን በመጠቀም አሳሳች መረጃዎችን በማሰራጨት ወንጀሉን እንደፈጸሙ ፖሊስ መግለፁን አንስተዋል።
የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ወንጀል ችሎት የቀረበው ክስ እንደሚያብራራው፣ ተጠርጣሪዎቹ ማንነታቸውን በመሰወርና ሀሰተኛ ሰነዶችን እና መታወቂያዎችን በማዘጋጀት እና በመጠቀም የተበዳዮችን ገንዘብ ለግል ጥቅማቸው አውለዋል።
በተጠርጣሪዎቹ ላይ የቀረበው ክስ በዋናነት በ1996 ዓ.ም የወጣውን የኢ.ፌ.ዲ.ሪ የወንጀል ሕግ እና የኮምፒዩተር ወንጀልን ለመደንገግ የወጣው አዋጅ ቁጥር 958/2008ን እንዲሁም የብሔራዊ የክፍያ ሥርዓት አዋጅ ቁጥር 718/2003ን የተላለፉ መሆናቸውን ይገልጻል።
ለወንጀል ድርጊቱ ማስፈጸሚያነት ሲጠቀሙባቸው የነበሩ በርካታ የባንክ አካውንቶች፣ የሞባይል ቀፎዎች፣ ሲም ካርዶች እና ኮምፒውተሮች እንደተያዙ ተገልጿል፡፡
ጉዳዩን ለማጣራትም ተጨማሪ ምርመራ እየተካሄደ መሆኑን የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ አስታውቋል።
በሀምራዊት ብርሀኑ
#ethiopia | በሞባይል ባንኪንግ ማጭበርበር ወንጀል በተጠረጠሩ 80 ግለሰቦች ላይ የፌደራል ዐቃቤ ሕግ ክስ እንደመሰረተ የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ተገልጿል።
ይህ የተገለጸው የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ የ2016/2017 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈፃፀምን ከተለያዩ የዘርፉ ተጠሪዎች ጋር እየገመገመ ባለበት መድረክ ላይ ነው።
የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ የወንጀል ምርመራ ጠቅላይ መምሪያ ተወካይ አቶ ሙሊሳ አብዲሳ ባቀረቡት ሪፖርት፣ በሞባይል ባንኪንግ አማካኝነት ከ116 ግለሰቦች ላይ ከ30 ሚሊዮን ብር በላይ በሞባይል ባንኪግ በማጭበርበር ወንጀል በተጠረጠሩ 80 ግለሰቦች ላይ የፌደራል ዐቃቤ ሕግ ክስ እንደተመሰረተባቸውገልጸዋል።
ተከሳሾቹ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ከሌሎች የግል ባንኮች የሚደውሉ በማስመሰል እንዲሁም የኮምፒውተር ሥርዓትን በመጠቀም አሳሳች መረጃዎችን በማሰራጨት ወንጀሉን እንደፈጸሙ ፖሊስ መግለፁን አንስተዋል።
የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ወንጀል ችሎት የቀረበው ክስ እንደሚያብራራው፣ ተጠርጣሪዎቹ ማንነታቸውን በመሰወርና ሀሰተኛ ሰነዶችን እና መታወቂያዎችን በማዘጋጀት እና በመጠቀም የተበዳዮችን ገንዘብ ለግል ጥቅማቸው አውለዋል።
በተጠርጣሪዎቹ ላይ የቀረበው ክስ በዋናነት በ1996 ዓ.ም የወጣውን የኢ.ፌ.ዲ.ሪ የወንጀል ሕግ እና የኮምፒዩተር ወንጀልን ለመደንገግ የወጣው አዋጅ ቁጥር 958/2008ን እንዲሁም የብሔራዊ የክፍያ ሥርዓት አዋጅ ቁጥር 718/2003ን የተላለፉ መሆናቸውን ይገልጻል።
ለወንጀል ድርጊቱ ማስፈጸሚያነት ሲጠቀሙባቸው የነበሩ በርካታ የባንክ አካውንቶች፣ የሞባይል ቀፎዎች፣ ሲም ካርዶች እና ኮምፒውተሮች እንደተያዙ ተገልጿል፡፡
ጉዳዩን ለማጣራትም ተጨማሪ ምርመራ እየተካሄደ መሆኑን የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ አስታውቋል።
በሀምራዊት ብርሀኑ
1 year ago
ከባንክ የተደወለ በማስመሰል ህዝቡን ሲዘርፉ የነበሩት 80 ግለሰቦች ላይ ክስ ተመሰረተ
#fastmereja I በሞባይል ባንኪንግ ወንጀል በተጠረጠሩ 80 ግለሰቦች ላይ ክስ ተመስርቶባቸዋል።
የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ በሞባይል ባንኪንግ አማካኝነት ከ116 ግለሰቦች ላይ ከ30 ሚሊዮን ብር በላይ በሞባይል ባንኪግ በማጭበርበር ወንጀል በተጠረጠሩ 80 ግለሰቦች ላይ ወንጀል ምርመራ በማጣራት ለፌደራል ዐቃቤ ህግ በማስተላለፍ ክስ እንዲመሰረት አድርጓል።
ተከሳሾቹ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ከሌሎች የግል ባንኮች የሚደውሉ በማስመሰል እንዲሁም የኮምፒውተር ስርዓትን በመጠቀም አሳሳች መረጃዎችን በማሰራጨት ወንጀሉን እንደፈጸሙ ፖሊስ ገልጿል።
የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ወንጀል ችሎት የቀረበው ክስ እንደሚያብራራው፣ ተጠርጣሪዎቹ ማንነታቸውን በመሰወር፣ ሀሰተኛ ሰነዶችን እና መታወቂያዎችን በማዘጋጀት እና በመጠቀም የተበዳዮችን ገንዘብ ለግል ጥቅማቸው ማዋላቸው በምርመራ ተረጋግጧል።
በተጠርጣሪዎቹ ላይ የቀረበው ክስ በዋናነት በ1996 ዓ.ም የወጣውን የኢ.ፌ.ዲ.ሪ የወንጀል ህግ እና የኮምፒዩተር ወንጀል አዋጅ ቁጥር 958/2008ን እንዲሁም የብሄራዊ የክፍያ ስርዓት አዋጅ ቁጥር 718/2003ን የተላለፉ መሆናቸውን ታውቋል።
ለወንጀል ድርጊቱ ማስፈጸሚያነት ሲጠቀሙባቸው የነበሩ በርካታ የባንክ አካውንቶች፣ የሞባይል ቀፎዎች፣ ሲም ካርዶች እና ኮምፒውተሮች የተያዙ ሲሆን፣ ጉዳዩን ለማጣራት ተጨማሪ ምርመራ እየተካሄደ መሆኑን የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ገልጿል።
በክሱ ከተጠቀሱት ተጠርጣሪዎች መካከል፡-
1,ራያን አዳም መሀመድ፡
2,አስራት አስፋቸው የቦ/ሀብታሙ ገብሬ
3,ገለታ ገነም ገበሬ/አማን አበበ አምቦ፣ አቤል አለማየሁ፣ ታምሩ ዘውዴ/፡
4,አክሊሉ አየለ አላቶ/አገኘው አየለ አደፎ/፡
5,ጌታቸው የኔው በሬ/ ታምራት ታከለ ገብሬ/
6,አሻግሬ ኬሮ አላቶ፡
7,ዋለልኝ ማሰሬ አበጀ፡
8,ቅዱስ ያሬድ ግርማዬ
9,አሸናፊ ሰለሞን ቸሩ፡
10,እንየው ተሰራ ዳኜው፡
11,ቃለአብ ታየ እታለማሁ
12,ዳንኤል ከበደ አያና፡
13,ድሪባ በቀለ ለማ
14,ጋሻው ታገለ ቢሻው፡
15,ተመስገን ተሰማ ፋንታሁን
16,አቤል ወንዱ ተከል፡
17,ረድኤት ደረጀ ፀጋ፡
18,አማኑ አንተነህ ሙላት/ ታዲዎስ መንጌሻ መኩሪያ/
19, አይናለም አንሙት ታደሰ፡
20, ቤቲ አደመ አንጋሞ/አዲስዓለም አደመ አንጋሞ/፡
21,ብርቱካን ሀይሌ ገ/ሚካኤል/አስቴር አበበ ግበሬ፣ አበዛሽ አለማየሁ/
22,ከይረዲን ሁሴን ፎጌ/ከይረዲን ጀማል ሳላ/
23,ሙሉዓለም መከተ ተፈራ፡
24,ብሩክ ጌታቸው ይርዳው
25, ዳንኤል ተስፋዬ በቀለ፡ -
26,ሚኪያስ ሔኖክ ባይዶ፡
27,ታምሩ ገ/የሱስ የባ/ሳሙኤል ገሮ የባ፣ ዮሐንስ ገረው የባ/
28,ታምራት እሸቱ ሀይሌ፡-
29, አሲያ ሁሴን መሀመድ/ኢሲያ ሁሴን አባዲኮ
30,ሳሙኤል ላጵሶ ዳለሎ
ህብረተሰቡ ከማያውቋቸው እና አጠራጣሪ ከሆኑ የስልክ ጥሪዎችና መልዕክቶች ራሱን እንዲጠብቅ ፖሊስ ጥሪ አቅርቧል።
ፌድራል ፖሊስ
#fastmereja I በሞባይል ባንኪንግ ወንጀል በተጠረጠሩ 80 ግለሰቦች ላይ ክስ ተመስርቶባቸዋል።
የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ በሞባይል ባንኪንግ አማካኝነት ከ116 ግለሰቦች ላይ ከ30 ሚሊዮን ብር በላይ በሞባይል ባንኪግ በማጭበርበር ወንጀል በተጠረጠሩ 80 ግለሰቦች ላይ ወንጀል ምርመራ በማጣራት ለፌደራል ዐቃቤ ህግ በማስተላለፍ ክስ እንዲመሰረት አድርጓል።
ተከሳሾቹ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ከሌሎች የግል ባንኮች የሚደውሉ በማስመሰል እንዲሁም የኮምፒውተር ስርዓትን በመጠቀም አሳሳች መረጃዎችን በማሰራጨት ወንጀሉን እንደፈጸሙ ፖሊስ ገልጿል።
የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ወንጀል ችሎት የቀረበው ክስ እንደሚያብራራው፣ ተጠርጣሪዎቹ ማንነታቸውን በመሰወር፣ ሀሰተኛ ሰነዶችን እና መታወቂያዎችን በማዘጋጀት እና በመጠቀም የተበዳዮችን ገንዘብ ለግል ጥቅማቸው ማዋላቸው በምርመራ ተረጋግጧል።
በተጠርጣሪዎቹ ላይ የቀረበው ክስ በዋናነት በ1996 ዓ.ም የወጣውን የኢ.ፌ.ዲ.ሪ የወንጀል ህግ እና የኮምፒዩተር ወንጀል አዋጅ ቁጥር 958/2008ን እንዲሁም የብሄራዊ የክፍያ ስርዓት አዋጅ ቁጥር 718/2003ን የተላለፉ መሆናቸውን ታውቋል።
ለወንጀል ድርጊቱ ማስፈጸሚያነት ሲጠቀሙባቸው የነበሩ በርካታ የባንክ አካውንቶች፣ የሞባይል ቀፎዎች፣ ሲም ካርዶች እና ኮምፒውተሮች የተያዙ ሲሆን፣ ጉዳዩን ለማጣራት ተጨማሪ ምርመራ እየተካሄደ መሆኑን የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ገልጿል።
በክሱ ከተጠቀሱት ተጠርጣሪዎች መካከል፡-
1,ራያን አዳም መሀመድ፡
2,አስራት አስፋቸው የቦ/ሀብታሙ ገብሬ
3,ገለታ ገነም ገበሬ/አማን አበበ አምቦ፣ አቤል አለማየሁ፣ ታምሩ ዘውዴ/፡
4,አክሊሉ አየለ አላቶ/አገኘው አየለ አደፎ/፡
5,ጌታቸው የኔው በሬ/ ታምራት ታከለ ገብሬ/
6,አሻግሬ ኬሮ አላቶ፡
7,ዋለልኝ ማሰሬ አበጀ፡
8,ቅዱስ ያሬድ ግርማዬ
9,አሸናፊ ሰለሞን ቸሩ፡
10,እንየው ተሰራ ዳኜው፡
11,ቃለአብ ታየ እታለማሁ
12,ዳንኤል ከበደ አያና፡
13,ድሪባ በቀለ ለማ
14,ጋሻው ታገለ ቢሻው፡
15,ተመስገን ተሰማ ፋንታሁን
16,አቤል ወንዱ ተከል፡
17,ረድኤት ደረጀ ፀጋ፡
18,አማኑ አንተነህ ሙላት/ ታዲዎስ መንጌሻ መኩሪያ/
19, አይናለም አንሙት ታደሰ፡
20, ቤቲ አደመ አንጋሞ/አዲስዓለም አደመ አንጋሞ/፡
21,ብርቱካን ሀይሌ ገ/ሚካኤል/አስቴር አበበ ግበሬ፣ አበዛሽ አለማየሁ/
22,ከይረዲን ሁሴን ፎጌ/ከይረዲን ጀማል ሳላ/
23,ሙሉዓለም መከተ ተፈራ፡
24,ብሩክ ጌታቸው ይርዳው
25, ዳንኤል ተስፋዬ በቀለ፡ -
26,ሚኪያስ ሔኖክ ባይዶ፡
27,ታምሩ ገ/የሱስ የባ/ሳሙኤል ገሮ የባ፣ ዮሐንስ ገረው የባ/
28,ታምራት እሸቱ ሀይሌ፡-
29, አሲያ ሁሴን መሀመድ/ኢሲያ ሁሴን አባዲኮ
30,ሳሙኤል ላጵሶ ዳለሎ
ህብረተሰቡ ከማያውቋቸው እና አጠራጣሪ ከሆኑ የስልክ ጥሪዎችና መልዕክቶች ራሱን እንዲጠብቅ ፖሊስ ጥሪ አቅርቧል።
ፌድራል ፖሊስ
1 year ago
በሞባይል ባንኪንግ ወንጀል በተጠረጠሩ 20 ግለሰቦች ላይ ክስ ተመሰረተ::
በሞባይል ባንኪንግ ወንጀል በተጠረጠሩ 20 ግለሰቦች ላይ ክስ ተመስርቶባቸዋል።
የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ በሞባይል ባንኪንግ አማካኝነት ከ116 ግለሰቦች ላይ ከ30 ሚሊዮን ብር በላይ በሞባይል ባንኪግ በማጭበርበር ወንጀል በተጠረጠሩ 20 ግለሰቦች ላይ የፌደራል ዐቃቤ ህግ ክስ መስርቶባቸዋል።
ተከሳሾቹ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ከሌሎች የግል ባንኮች የሚደውሉ በማስመሰል እንዲሁም የኮምፒውተር ስርዓትን በመጠቀም አሳሳች መረጃዎችን በማሰራጨት ወንጀሉን እንደፈጸሙ ፖሊስ ገልጿል።
የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ወንጀል ችሎት የቀረበው ክስ እንደሚያብራራው፣ ተጠርጣሪዎቹ ማንነታቸውን በመሰወርና ሀሰተኛ ሰነዶችን እና መታወቂያዎችን በማዘጋጀት እና በመጠቀም የተበዳዮችን ገንዘብ ለግል ጥቅማቸው አውለዋል።
በተጠርጣሪዎቹ ላይ የቀረበው ክስ በዋናነት በ1996 ዓ.ም የወጣውን የኢ.ፌ.ዲ.ሪ የወንጀል ህግ እና የኮምፒዩተር ወንጀል አዋጅ ቁጥር 958/2008ን እንዲሁም የብሄራዊ የክፍያ ስርዓት አዋጅ ቁጥር 718/2003ን የተላለፉ መሆናቸውን ይገልጻል።
ለወንጀል ድርጊቱ ማስፈጸሚያነት ሲጠቀሙባቸው የነበሩ በርካታ የባንክ አካውንቶች፣ የሞባይል ቀፎዎች፣ ሲም ካርዶች እና ኮምፒውተሮች የተያዙ ሲሆን፣ ጉዳዩን ለማጣራት ተጨማሪ ምርመራ እየተካሄደ መሆኑን የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ አስታውቋል።
በክሱ ከተጠቀሱት ተጠርጣሪዎች መካከል፡-
1,ራያን አዳም መሀመድ፡
2,አስራት አስፋቸው የቦ/ሀብታሙ ገብሬ
3,ገለታ ገነም ገበሬ/አማን አበበ አምቦ፣ አቤል አለማየሁ፣ ታምሩ ዘውዴ/፡
4,አክሊሉ አየለ አላቶ/አገኘው አየለ አደፎ/፡
5,ጌታቸው የኔው በሬ/ ታምራት ታከለ ገብሬ/
6,አሻግሬ ኬሮ አላቶ፡
7,ዋለልኝ ማሰሬ አበጀ፡
8,ቅዱስ ያሬድ ግርማዬ
9,አሸናፊ ሰለሞን ቸሩ፡
10,እንየው ተሰራ ዳኜው፡
11,ቃለአብ ታየ እታለማሁ
12,ዳንኤል ከበደ አያና፡
13,ድሪባ በቀለ ለማ
14,ጋሻው ታገለ ቢሻው፡
15,ተመስገን ተሰማ ፋንታሁን
16,አቤል ወንዱ ተከል፡
17,ረድኤት ደረጀ ፀጋ፡
18,አማኑ አንተነህ ሙላት/ ታዲዎስ መንጌሻ መኩሪያ/
19, አይናለም አንሙት ታደሰ፡
20, ቤቲ አደመ አንጋሞ/አዲስዓለም አደመ አንጋሞ/፡
21,ብርቱካን ሀይሌ ገ/ሚካኤል/አስቴር አበበ ግበሬ፣ አበዛሽ አለማየሁ/
22,ከይረዲን ሁሴን ፎጌ/ከይረዲን ጀማል ሳላ/
23,ሙሉዓለም መከተ ተፈራ፡
24,ብሩክ ጌታቸው ይርዳው
25, ዳንኤል ተስፋዬ በቀለ፡ -
26,ሚኪያስ ሔኖክ ባይዶ፡
27,ታምሩ ገ/የሱስ የባ/ሳሙኤል ገሮ የባ፣ ዮሐንስ ገረው የባ/
28,ታምራት እሸቱ ሀይሌ፡-
29, አሲያ ሁሴን መሀመድ/ኢሲያ ሁሴን አባዲኮ
30,ሳሙኤል ላጵሶ ዳለሎ
ህብረተሰቡ ከማያውቋቸው እና አጠራጣሪ ከሆኑ የስልክ ጥሪዎችና መልዕክቶች ራሱን እንዲጠብቅ ጥሪ አቅርቧል።
Via ኢፌፖሚ
በሞባይል ባንኪንግ ወንጀል በተጠረጠሩ 20 ግለሰቦች ላይ ክስ ተመስርቶባቸዋል።
የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ በሞባይል ባንኪንግ አማካኝነት ከ116 ግለሰቦች ላይ ከ30 ሚሊዮን ብር በላይ በሞባይል ባንኪግ በማጭበርበር ወንጀል በተጠረጠሩ 20 ግለሰቦች ላይ የፌደራል ዐቃቤ ህግ ክስ መስርቶባቸዋል።
ተከሳሾቹ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ከሌሎች የግል ባንኮች የሚደውሉ በማስመሰል እንዲሁም የኮምፒውተር ስርዓትን በመጠቀም አሳሳች መረጃዎችን በማሰራጨት ወንጀሉን እንደፈጸሙ ፖሊስ ገልጿል።
የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ወንጀል ችሎት የቀረበው ክስ እንደሚያብራራው፣ ተጠርጣሪዎቹ ማንነታቸውን በመሰወርና ሀሰተኛ ሰነዶችን እና መታወቂያዎችን በማዘጋጀት እና በመጠቀም የተበዳዮችን ገንዘብ ለግል ጥቅማቸው አውለዋል።
በተጠርጣሪዎቹ ላይ የቀረበው ክስ በዋናነት በ1996 ዓ.ም የወጣውን የኢ.ፌ.ዲ.ሪ የወንጀል ህግ እና የኮምፒዩተር ወንጀል አዋጅ ቁጥር 958/2008ን እንዲሁም የብሄራዊ የክፍያ ስርዓት አዋጅ ቁጥር 718/2003ን የተላለፉ መሆናቸውን ይገልጻል።
ለወንጀል ድርጊቱ ማስፈጸሚያነት ሲጠቀሙባቸው የነበሩ በርካታ የባንክ አካውንቶች፣ የሞባይል ቀፎዎች፣ ሲም ካርዶች እና ኮምፒውተሮች የተያዙ ሲሆን፣ ጉዳዩን ለማጣራት ተጨማሪ ምርመራ እየተካሄደ መሆኑን የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ አስታውቋል።
በክሱ ከተጠቀሱት ተጠርጣሪዎች መካከል፡-
1,ራያን አዳም መሀመድ፡
2,አስራት አስፋቸው የቦ/ሀብታሙ ገብሬ
3,ገለታ ገነም ገበሬ/አማን አበበ አምቦ፣ አቤል አለማየሁ፣ ታምሩ ዘውዴ/፡
4,አክሊሉ አየለ አላቶ/አገኘው አየለ አደፎ/፡
5,ጌታቸው የኔው በሬ/ ታምራት ታከለ ገብሬ/
6,አሻግሬ ኬሮ አላቶ፡
7,ዋለልኝ ማሰሬ አበጀ፡
8,ቅዱስ ያሬድ ግርማዬ
9,አሸናፊ ሰለሞን ቸሩ፡
10,እንየው ተሰራ ዳኜው፡
11,ቃለአብ ታየ እታለማሁ
12,ዳንኤል ከበደ አያና፡
13,ድሪባ በቀለ ለማ
14,ጋሻው ታገለ ቢሻው፡
15,ተመስገን ተሰማ ፋንታሁን
16,አቤል ወንዱ ተከል፡
17,ረድኤት ደረጀ ፀጋ፡
18,አማኑ አንተነህ ሙላት/ ታዲዎስ መንጌሻ መኩሪያ/
19, አይናለም አንሙት ታደሰ፡
20, ቤቲ አደመ አንጋሞ/አዲስዓለም አደመ አንጋሞ/፡
21,ብርቱካን ሀይሌ ገ/ሚካኤል/አስቴር አበበ ግበሬ፣ አበዛሽ አለማየሁ/
22,ከይረዲን ሁሴን ፎጌ/ከይረዲን ጀማል ሳላ/
23,ሙሉዓለም መከተ ተፈራ፡
24,ብሩክ ጌታቸው ይርዳው
25, ዳንኤል ተስፋዬ በቀለ፡ -
26,ሚኪያስ ሔኖክ ባይዶ፡
27,ታምሩ ገ/የሱስ የባ/ሳሙኤል ገሮ የባ፣ ዮሐንስ ገረው የባ/
28,ታምራት እሸቱ ሀይሌ፡-
29, አሲያ ሁሴን መሀመድ/ኢሲያ ሁሴን አባዲኮ
30,ሳሙኤል ላጵሶ ዳለሎ
ህብረተሰቡ ከማያውቋቸው እና አጠራጣሪ ከሆኑ የስልክ ጥሪዎችና መልዕክቶች ራሱን እንዲጠብቅ ጥሪ አቅርቧል።
Via ኢፌፖሚ
1 year ago
በሞባይል ባንኪንግ ማጭበርበር ወንጀል በተጠረጠሩ 20 ግለሰቦች ላይ የፌደራል ዐቃቤ ሕግ ክስ መመስረቱን የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ አስታወቀ
ይህ የተገለጸው የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ የ2016/2017 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈፃፀምን ከተለያዩ የዘርፉ ተጠሪዎች ጋር እየገመገመ ባለበት መድረክ ላይ ነው።
የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ የወንጀል ምርመራ ጠቅላይ መምሪያ ተወካይ አቶ ሙሊሳ አብዲሳ ባቀረቡት ሪፖርት፣ በሞባይል ባንኪንግ አማካኝነት ከ116 ግለሰቦች ላይ ከ30 ሚሊዮን ብር በላይ በሞባይል ባንኪግ በማጭበርበር ወንጀል በተጠረጠሩ 20 ግለሰቦች ላይ የፌደራል ዐቃቤ ሕግ ክስ እንደተመሰረተባቸው ገልጸዋል።
ተከሳሾቹ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ከሌሎች የግል ባንኮች የሚደውሉ በማስመሰል እንዲሁም የኮምፒውተር ሥርዓትን በመጠቀም አሳሳች መረጃዎችን በማሰራጨት ወንጀሉን እንደፈጸሙ ፖሊስ መግለጹን አንስተዋል።
የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ወንጀል ችሎት የቀረበው ክስ እንደሚያብራራው፤ ተጠርጣሪዎቹ ማንነታቸውን በመሰወርና ሀሰተኛ ሰነዶችን እና መታወቂያዎችን በማዘጋጀት እና በመጠቀም የተበዳዮችን ገንዘብ ለግል ጥቅማቸው አውለዋል።
በተጠርጣሪዎቹ ላይ የቀረበው ክስ በዋናነት በ1996 ዓ.ም የወጣውን የኢ.ፌ.ዲ.ሪ የወንጀል ሕግ እና የኮምፒዩተር ወንጀልን ለመደንገግ የወጣው አዋጅ ቁጥር 958/2008ን እንዲሁም የብሔራዊ የክፍያ ሥርዓት አዋጅ ቁጥር 718/2003ን የተላለፉ መሆናቸውን ይገልጻል።
ለወንጀል ድርጊቱ ማስፈጸሚያነት ሲጠቀሙባቸው የነበሩ በርካታ የባንክ አካውንቶች፣ የሞባይል ቀፎዎች፣ ሲም ካርዶች እና ኮምፒውተሮች እንደተያዙ መገለጹን የኢቢሲ ዘገባ አመላቷል፡፡
ጉዳዩን ለማጣራትም ተጨማሪ ምርመራ እየተካሄደ መሆኑን የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ አስታውቋል።
Seledadotio
Seledadotio
ይህ የተገለጸው የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ የ2016/2017 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈፃፀምን ከተለያዩ የዘርፉ ተጠሪዎች ጋር እየገመገመ ባለበት መድረክ ላይ ነው።
የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ የወንጀል ምርመራ ጠቅላይ መምሪያ ተወካይ አቶ ሙሊሳ አብዲሳ ባቀረቡት ሪፖርት፣ በሞባይል ባንኪንግ አማካኝነት ከ116 ግለሰቦች ላይ ከ30 ሚሊዮን ብር በላይ በሞባይል ባንኪግ በማጭበርበር ወንጀል በተጠረጠሩ 20 ግለሰቦች ላይ የፌደራል ዐቃቤ ሕግ ክስ እንደተመሰረተባቸው ገልጸዋል።
ተከሳሾቹ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ከሌሎች የግል ባንኮች የሚደውሉ በማስመሰል እንዲሁም የኮምፒውተር ሥርዓትን በመጠቀም አሳሳች መረጃዎችን በማሰራጨት ወንጀሉን እንደፈጸሙ ፖሊስ መግለጹን አንስተዋል።
የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ወንጀል ችሎት የቀረበው ክስ እንደሚያብራራው፤ ተጠርጣሪዎቹ ማንነታቸውን በመሰወርና ሀሰተኛ ሰነዶችን እና መታወቂያዎችን በማዘጋጀት እና በመጠቀም የተበዳዮችን ገንዘብ ለግል ጥቅማቸው አውለዋል።
በተጠርጣሪዎቹ ላይ የቀረበው ክስ በዋናነት በ1996 ዓ.ም የወጣውን የኢ.ፌ.ዲ.ሪ የወንጀል ሕግ እና የኮምፒዩተር ወንጀልን ለመደንገግ የወጣው አዋጅ ቁጥር 958/2008ን እንዲሁም የብሔራዊ የክፍያ ሥርዓት አዋጅ ቁጥር 718/2003ን የተላለፉ መሆናቸውን ይገልጻል።
ለወንጀል ድርጊቱ ማስፈጸሚያነት ሲጠቀሙባቸው የነበሩ በርካታ የባንክ አካውንቶች፣ የሞባይል ቀፎዎች፣ ሲም ካርዶች እና ኮምፒውተሮች እንደተያዙ መገለጹን የኢቢሲ ዘገባ አመላቷል፡፡
ጉዳዩን ለማጣራትም ተጨማሪ ምርመራ እየተካሄደ መሆኑን የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ አስታውቋል።
Seledadotio
Seledadotio
Sponsored by
Surafel
Comments