Logo
Getu Temesgen
በኢትዮጵያ ዘመናዊ ውትድርና ታሪክ አንድ የታሪክ ምዕራፍ ተዘጋ

ከአለባቸው ደሳለኝ አበሻ (ለንደን)
#ethiopia | ዶ/ር ሜ/ጄኔራ መስፍን ገብረ ቃል የኢትዮጵያ መለያ ምልክት August 1937 ተወለዱ August
2025 በተወለዱ 88 አመታቸው ከዚህ አለም በሞት ተለየ ።

August 28 /2025 በእንግሊዝ ሐገር በለንደን ከተማ
የቀብር ስነስርአታቸው ተፈፀመ።

ዶ/ር ሜ/ጄኔራ መስፍን ገብረ ቃል
በኖሩባቸው በእነዚህ አመታቶች ውስጥ ከባለቤታቸው ከወ/ሮ ሙሉ ተ/ብርሀን አራት ልጆችን አፍርተዋል

የትምሕርት ዝግጅታቸውን በተመለከተ ፤

*በ1958 ዓ/ም በቀዳማዊ ሐይለስላሴ ዘመነ መንግስት ከተመረጡት ሁለት ተማሪወች አንዱ በመሆን እንግሊዝ አገር ከሳናደርስት ሮያል ወታደራዊ አካዳሚ ከፍተኛ ወታደራዊ ትምህርት ተምረው ተመርቀዋል ።

*በ1668 አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ በሕግ ዲግሪ ተመርቀዋል።

*በ1969 Camberley British Army staff College (P.S.C)

*በ1996 ከኪንግስ ኮለጅ ለንደን የጦርነት ጥናቶች ክፍል የማስተር ዲግሪ (MA)department of War studies

*2002 ፒኤችዲ (PHD) የአፍሪካ ቀንድ : ከቀዝቃዛው ጦርነት በሗላ የደህንነት ተለዋዋጭ ባህሪ (the horn of africa challenging nature off security in the aftermath of the cold War) ዲግሪያቸው ተቀብለዋል ።

ዶ/ር ሜ/ጄኔራ መስፍን ገብረ ቃል በህይወት ዘመናቸዉ ከተለያዩ ከፍተኛ የመንግስት ተቋማት ልዩ ልዩ ሽልማቶችን ተቀብለዋል ።

* ከተባበሩት መንግስታት የአገልግሎት ሜዳሊያ ።
(UN service medal)
ኮንጎ የሠላም ሜዳል
(Congo peace medal)
የሁለት ናይሎች ትዕዛዝ በሡዳኑ ፕሬዝዳንት ኑሜሪ ተሸልመዋል
(Order of the two Nile by president numeri of the Sudan )

* ከ1977- 1978 በኢትዮጵያና በአጎራባቿ ሡማሊያ በተደረገው ከፍተኛ ጦርነት በሠጡት ወታደራዊ አመራር የኢትዮጵያ አንደኛ ደረጃ የጀግና ሜዳይ ተሸላሚ ነበሩ ።

ዶ/ር ሜ/ጄኔራ መስፍን ገብረ ቃል
በኢትዮጵያ ውስጥ ብቻ ሳይሆን በተባበሩት መንግስታት የሠላም አስከባሪ በመሆን ለአደረጉት አስተዋፅዎ ከፍተኛ ምስጋናን ተቀብለዋል ።

ዶ/ር ሜ/ጄኔራ መስፍን ገብረ ቃል
ብዙ አስቸጋሪ የህይወት ውጣ ውረድ በሚታይበት ወታደራዊ ሞያ ሙሉ ሕይወታቸውን ለኢትዮጵያ አገራቸው ሰተው አልፈዋል ::

ዶ/ር ሜ/ጄኔራ መስፍን ገብረ ቃል
በጥይት እርሳስ እየተቆሉ በቦንብ ውርጅብኝ መላ አካላታቸው እየነደደ ላንቃቸው እሳት በሚተፉ ከባድና ቀላል መሳሪያዎች በግንባርና በደረታቸው በእግርና በእጃቸው በመላ አካላታቸው ላይ ጥይቶች እያራገፉባቸው ደማቸውን አፍስሰው ህይወታቸውን ከገብሩት የቀድሞ የኢትዮጵያ ሰራዊት ጎን ተሠልፈው ለኢትዮጵያ አንድነት ከታገሉት ከፍተኛ የጦር አዛዦች አንዱ ነበሩ።

ዶ/ር ሜ/ጄኔራ መስፍን ገብረ ቃል
የሶስት ሽህ ዘመን የታሪክ አውራ የሆነች ታላቅ ሐገራቸው ኢትዮጰያ ህልውናዋን፣ ማስቀጠል ደንበሯን መጠበቅ የታሪክ ሀላፊነት በሳቸውና በጓዶቻቸው እጅ ሲወድቅ
ግንቦት 19 ቀን 1983 ከቀድሞ የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ተስፋዬ ዲንቃ ጋር በመሆን ከሻዕቢያ፣ እንዲሁም ከወያኔና ከኦሮሞ ነጻነት ግንባር ጋር ሊካሄድ በታቀደው ድርድር ለመሳተፍ የመንግስት ልዑካን ከነበሩት አንዱ በመሆን ለድርድር እንግሊዝ አገር ለንደን ገቡ ።

በአሜሪካን መንግስት የተመራው የሽምግልና ድርድር ኤርትራን አስገንጥሎ ወያኔን ኢትዮጵያ ላይ አንግሶ በአሳዛኝ ሁኔታ ያለ ውጤት ተደመደመ ።

ዶ/ር ሜ/ጄኔራ መስፍን ገብረ ቃል ወደሐገራቸው ሳይመለሡ
ህይወታቸው እሰከአለፈበት ነሐሴ 11/2025 ድረስ ከ30 አመት በላይ በስደት እንግሊዝ አገር ኑረዋል።

በመጨረሻ ግን ሕይወታቸው ካለፈ በሗላ በቤተሠቦቻቸው ምርጫ ለክብሯ ቆመው በነፍስ በሥጋ በአጥንት በደም ታላቅን የማይተካ ክቡር መስዋዕትነት፣ ታላቅን ውድ ሕይወታቸውን ከፍለው ኢትዮጵያ እድተቀጥል ያደረጉት ጀግና
ዶ/ር ሜ/ጄኔራ መስፍን ገብረ ቃል
የኸደፊቱን መገመት ባልችልም
በባዕድ አገር አስከሬናቸው ሲቀር እንደዜጋ ልቤ ተሰብሮ አልቅሻለሁ ።

የኢትዮጵያ ጀግኖች አደራ ውስጡ ድረስ ዘልቆ የሚሰማው የትኛውም ባለአደራ ትውልድ፣ እንደ ዶ/ር
ሜ/ጄኔራ መስፍን ገብረ ቃል የመሳሰሉ ጀግኖች ለኢትዮጵያ አንድነት የከፈሉለትን የነፃነት ዋጋ
ታሳቢ በማድረግ አፅማቸው በትውልድ ሐገራቸው እንዲያርፍ የማድረግ ትልቅ ሐላፊነት አለበት ብየ አምናለሁ ።

ወዳጆቼ !!
ከተሳካልኝ ወደፊት ቤተሠቦቻቸውን አነጋግሬ በሠፊው እመለስበታለሁ ።
እስከዚያው ቸር ያቆየን ።

11 months ago

No replys yet!

Be the first to share what you think — your comment will appear here.