9 hours ago
♦️በተተኮሠበት ጥይት ተመቶ ህይወቱ ባለፈው የቀድሞ አትሌት ይሄይስ ታደለው ዙሪያ የተጠናከረ ልዩ ዘገባ
♦️በአትሌቶች መካከል ያለውን የአጉል ባህልና ዕምነት፣የመጠራጠርና የመጠፋፋት ባህል እንደወረርሽኝ ተዛምቶ ለተጨማሪ አደጋ ከመጋለጣችን በፊት ይታሰብበት
✍️✍️በጋዜጠኛ ይስሀቅ በላይ(ሀትሪክ ስፖርት ኦፊሺያል)
♦️የሟችና በገዳይነት የተጠረጠረው አትሌት ማንነት
በሚያሳዝን ሁኔታ ሁለቱም የነገ ውጤታማ አትሌቶች ይሆናሉ ተብሎ ተስፋ የተጣለባቸው ወጣቶች ነበሩ፤ጉዳዩ በህግ የተያዘ በመሆኑና በማስረጃ የተረጋገጠ ነገር ባይኖርም ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው ወገኖች በተለይ ለሀትሪክ እንደገለፁት በገዳይነት ተጠርጥሮ በህግ ቁጥጥር ስር የሚገኘው አትሌት ደረሠ ረታ ከደብረብርሃን የተገኘ በመቀጠል በፌዴራል ማረሚያ ቤቶች አሁን በመጨረሻ ደግሞ ለፌዴራል ፖሊስ የሚሮጥ አትሌት ሲሆን በጣም ትልቅ ተስፋ የተጣለበት አትሌት እንደነበረም ነው ለአትሌቱ ቅርበት ያላቸው ወገኖች የሚናገሩት።እንደ እነዚሁ ምንጮቻችን አገላለፅ አትሌቱ ከአንድ ዓመት በፊት በጉያንግ በተካሄደው ውድድር 2:12:00 በሆነ ሠዓት በመግባት የተሻለ ሠዓትና ደረጃ ይዞ ያጠናቀቀ ሲሆን የቅርብ ምርጥ ሠዓቱም 2:13:00 እንደሆነ ነው የሚሠማው።
በተተኮሠበት ጥይት ህይወቱ ያለፈው አትሌት ይሄይስ ታደለው በበኩሉ ከአማራ ክልል (ሠሜን ሸዋ)የተገኘ አትሌት ሲሆን በጉዳት ምክንያት ከውድድር ርቆ ባለቤቱን አትሌት ወርቅነሽ ዓለሙን እንደ አሠልጣኝ ሆኖ ከማሠራት ውጪ በአሁን ሠዓት በአትሌትነት እየሮጠ አይደለም።
♦️እስከመገዳደል ያደረሳቸው ምን ይሆን?
ሁለቱን ከአንድ ክልል የመጡ አትሌቶችን እስከመገዳደል ያበቃቸውን ትክክለኛውን ከእነሱና ከፈጣሪ ውጪ የሚያውቅ ሠው ፈልጎ ማግኘት አይቻልም፤ነገር በመካከላቸው ለገላጋይ ያስቸገረ አለመግባባት እኔዳላቸው ቀአሠልጣኝቻቸውና በቤተሠብቻቸው እኔዲሁም አትሌት በሆኑት ሚስቶቻቸው ጭምር ይታወቃል።የፀባቸውን መነሻ በትክክል መግለፅ ባይቻልም ከአጉልጰባህል ወይም አምልኮ ጋር ተያይዞ ባለቤቴና እኔ ላይ ይሄን አስደርገሃል የሚለው ዋነኛው የግጭታቸውና እስከመገዳደል ያደረሠ ችግር እንደሆነ በዙሪያ ያሉ ሠዎች ይናገራሉ፤ይህ ከድሮም ጀምሮ በአትሌቶች ዙሪያ የሚሠማው አጉል ባህል ወይም የአምልኮ ነገር ዛሬ ወደ አዲሶቹ ትውልዶችም ተሸጋግሮ አብሮ ልምምድ ያለመስራት፣አብሮ በህቴል እኔደጓደኛ አትሌት ክፍል ያለመጋራት፣አብሮ ያለመብላትና አብሮ በአንድ አውሮፕላን አልሄድም እስከማለት አስፈሪ ውሳኔ ላይ ተደርሶ የቡድን ስሜት ከአትሌቲክሱ እንዲጠፋ ምክንያት ሆኗል።
♦️ለሽማግሌና ለአስታራቂዎች ያስቸገሩት ሟችና ገዳይ
በሁለቱ አትሌትች መካከል ያለውን አለመግባባት ለመፍታት ያልመጣ አስታራቂ ሽማግሌ፣የሁለቱም አሠልጣኞች ፍቅሩና ኢማና መርጊያን ጨምሮ፣የቅርብ ጓደኛ በመጨረሻም ቤተሠብች የሁለቱንም አለመግባባት ለመፍታት ዳገት ቢወጡ ቁልቁል ቢወርዱ ሊሳካ አልቻለም፤አሠልጣኞችም ነገሩ ከብዷቸው ሁለቱም ሴት አትሌቶች በተለያየ አሠልጣኝ የተለያየ ቦታ እንዲሠሩ እሰከማድረግ ደርሠዋል፤በውስጥ የተቋጠረው ቂም በሽማግሌም፣በገላጋይ አልፈታም ብሎ በመጨረሻም ድምዳሜው የአንደኛው ህይወት በአንደኛው እጅ መጥፋት ሆኗል።
♦️የአትሌቱ ህይወት ስላለፈበት አጋጣሚ
ገዳይ እንዴትና የት፣በምን ሁኔታ የሟችን ህይወት ነጠቀ የሚለው ብዙዎች ለማወቅና እርግጠኛ መሆን የሚፈልጉበት ጥያቄ ነው፤በገዳይነት የተጠረጠረው አትሌት ደረሠ ረታ በውስጡ በተፈጠረ አንዳች ስሜት ተነሳስቶ ወደ ሠንዳፋ የልምምድ ቦታ ድንገት አመራ፤በዛች ቀን የተደገሠለትን ድግስና ከሞት ጋር ቀጠሮ እንዳለው ለሠከንድም ቢሆን ያላሠበው የቀድሞ አትሌት ይሄይስ ታደለው ባለቤቱን አትሌት ወርቅነሽ ዓለሙን ከፊት ሆኖ እያሠራ እያለ በድንገት በተተኮሠበት ጥይት ይህቺን ዓለም ዳግም ላይመለስባት ለዘለዓለሙ አሸልቧል።በገዳይነት የተጠረጠረው ከፊቱ በርካታ የአትሌቲክስ የስኬት ዓመታት እንዳሉት የሚነገርለት በግድያ የተጠረጠረው አትሌት ደረሠ ረታ ከግድያው በኋላ ራሱን ለማሸሽ ጥረት ቢያደርግም በአካባቢው በነበሩ አርሶ አደሮች ጥረት ተይዞ አሁን ሠንዳፋ በሚገኘው ማረሚያ ቤት በህግ ጥላ ስር ውሎ ጉዳዩን እየተከታተለ ይገኛል።
♦️"በጣም ተፈታተነኝ፣በጣም ታገለኝ"የሚል አጭር ቃል የተነፈሠው ገዳይ
በግድያ ተጠርጥሮ በህግ ጥላ ስር የሚገኘው አትሌት ደረሠ ረታ ከግድያው በኋላ በተለይ ዛሬ ከሟች አትሌት ይሄይስ ታደለው የቀብር ስነ-ስርዓቱ ከተፈፀመ በኋላ የቅርብ ወዳጆቹ ለምን እንደዚህ አይነት ውሳኔ እንደወሠነ ጠይቀውት ከገጠመው ያልታሠበ ፈተና ውስጥ የወደቀው አትሌቱ በፀፀት ውስጥ ሆኖ "በጣም ተፈታተነኝ፣በጣም ታገለኝ"የሚል አጭር ቃል ከመናገር የዘለለ መተንፈስ እንዳልቻለ ለሀትሪክ ስፖርት ኦፊሺያል ገልፀዋል።
♦️የአትሌት ይሄይስ ታደለው የመጨረሻ ስንብት
የአትሌት ይሄይስ ታደለው የቀብር ስነ-ስርዓቱና የአስከሬን ሽኝት ዛሬ ከቀኑ በ6:00 በሚኖሩበት ሠንዳፋ በኬ ማርያም ቤተክርስቲያን የአትሌቱ ቤተሠቦች፣ጓደኞች፣አሠልጣኞች፣አትሌቶችና የስፖርት ቤተሠቦች በተገኙበት በክብር አርፏል።በጉዳት ምክንያት ከአትሌቲክስ ርቆ ባለቤቱን በማሠራት የሚያሳልፈው አትሌት ይሄይስ ታደለው እንደዋዛ ይህቺን ዓለምና አትሌቲክሱንም ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ተሠናብቷል።
♦️ለኢት.አ.ፌዴሬሽንና ለአትዮጵያ አትሌቶች ማህበር መልዕክት
የኢት.አ.ፌዴሬሽንና የአትዮጵያ አትሌቶች ማህበር እስከአሁን በአሳዛኙ ክስተት ዙሪያ የተነፈሱት ነገር አለመኖሩ ትዝብትን ፈጥሯል፤እንደ ሀገርም እንደ አትሌቲክሱ ዓለምም ትልቅ ስብራትና ልብ ሠባሪ አጋጣሚ ነው፤ሁለቱም አካላት በአትሌቶቹ መካከል የተፈጠረውን ግድያ ወደ ሌሎች እንዳይዛመትና በዚሁ እንዲያበቃ በይፋ በመግለጫ ጭምር ማውገዝና ማስተማር ይጠበቅባቸዋል።ከዚህ በፊት በተመሳሳይ ምክንያቶች የጠፋውን ውዱን የሠው ልጅ ህይወት መለስ ብሎ ላስታወሠ በጎረቤት ኬንያ በጥይት አረር ህይወታቸው የተነጠቁ አትሌቶች፣አሠልጣኞችና የአትሌቶች ህይወት እንደዋዛ መነጠቁን በትዝታ ፈረስ ወደኋላ ሄዶ ላስታወሠ ጉዳዩ ቢያሳስበው አይፈረድበትም፤ይሄ በአትሌቶች መካከል ያለውን የአጉል ባህልና ዕምነት፣የመጠራጠርና የመጠፋፋት ባህል እንደወረርሽኝ ተዛምቶ ለተጨማሪ አደጋ ከመጋለጣችን በአሠልጣኞችና በአትሌቶች አእምሮ ላይ ስራ ይሠራ።
♦️በአትሌቶች መካከል ያለውን የአጉል ባህልና ዕምነት፣የመጠራጠርና የመጠፋፋት ባህል እንደወረርሽኝ ተዛምቶ ለተጨማሪ አደጋ ከመጋለጣችን በፊት ይታሰብበት
✍️✍️በጋዜጠኛ ይስሀቅ በላይ(ሀትሪክ ስፖርት ኦፊሺያል)
♦️የሟችና በገዳይነት የተጠረጠረው አትሌት ማንነት
በሚያሳዝን ሁኔታ ሁለቱም የነገ ውጤታማ አትሌቶች ይሆናሉ ተብሎ ተስፋ የተጣለባቸው ወጣቶች ነበሩ፤ጉዳዩ በህግ የተያዘ በመሆኑና በማስረጃ የተረጋገጠ ነገር ባይኖርም ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው ወገኖች በተለይ ለሀትሪክ እንደገለፁት በገዳይነት ተጠርጥሮ በህግ ቁጥጥር ስር የሚገኘው አትሌት ደረሠ ረታ ከደብረብርሃን የተገኘ በመቀጠል በፌዴራል ማረሚያ ቤቶች አሁን በመጨረሻ ደግሞ ለፌዴራል ፖሊስ የሚሮጥ አትሌት ሲሆን በጣም ትልቅ ተስፋ የተጣለበት አትሌት እንደነበረም ነው ለአትሌቱ ቅርበት ያላቸው ወገኖች የሚናገሩት።እንደ እነዚሁ ምንጮቻችን አገላለፅ አትሌቱ ከአንድ ዓመት በፊት በጉያንግ በተካሄደው ውድድር 2:12:00 በሆነ ሠዓት በመግባት የተሻለ ሠዓትና ደረጃ ይዞ ያጠናቀቀ ሲሆን የቅርብ ምርጥ ሠዓቱም 2:13:00 እንደሆነ ነው የሚሠማው።
በተተኮሠበት ጥይት ህይወቱ ያለፈው አትሌት ይሄይስ ታደለው በበኩሉ ከአማራ ክልል (ሠሜን ሸዋ)የተገኘ አትሌት ሲሆን በጉዳት ምክንያት ከውድድር ርቆ ባለቤቱን አትሌት ወርቅነሽ ዓለሙን እንደ አሠልጣኝ ሆኖ ከማሠራት ውጪ በአሁን ሠዓት በአትሌትነት እየሮጠ አይደለም።
♦️እስከመገዳደል ያደረሳቸው ምን ይሆን?
ሁለቱን ከአንድ ክልል የመጡ አትሌቶችን እስከመገዳደል ያበቃቸውን ትክክለኛውን ከእነሱና ከፈጣሪ ውጪ የሚያውቅ ሠው ፈልጎ ማግኘት አይቻልም፤ነገር በመካከላቸው ለገላጋይ ያስቸገረ አለመግባባት እኔዳላቸው ቀአሠልጣኝቻቸውና በቤተሠብቻቸው እኔዲሁም አትሌት በሆኑት ሚስቶቻቸው ጭምር ይታወቃል።የፀባቸውን መነሻ በትክክል መግለፅ ባይቻልም ከአጉልጰባህል ወይም አምልኮ ጋር ተያይዞ ባለቤቴና እኔ ላይ ይሄን አስደርገሃል የሚለው ዋነኛው የግጭታቸውና እስከመገዳደል ያደረሠ ችግር እንደሆነ በዙሪያ ያሉ ሠዎች ይናገራሉ፤ይህ ከድሮም ጀምሮ በአትሌቶች ዙሪያ የሚሠማው አጉል ባህል ወይም የአምልኮ ነገር ዛሬ ወደ አዲሶቹ ትውልዶችም ተሸጋግሮ አብሮ ልምምድ ያለመስራት፣አብሮ በህቴል እኔደጓደኛ አትሌት ክፍል ያለመጋራት፣አብሮ ያለመብላትና አብሮ በአንድ አውሮፕላን አልሄድም እስከማለት አስፈሪ ውሳኔ ላይ ተደርሶ የቡድን ስሜት ከአትሌቲክሱ እንዲጠፋ ምክንያት ሆኗል።
♦️ለሽማግሌና ለአስታራቂዎች ያስቸገሩት ሟችና ገዳይ
በሁለቱ አትሌትች መካከል ያለውን አለመግባባት ለመፍታት ያልመጣ አስታራቂ ሽማግሌ፣የሁለቱም አሠልጣኞች ፍቅሩና ኢማና መርጊያን ጨምሮ፣የቅርብ ጓደኛ በመጨረሻም ቤተሠብች የሁለቱንም አለመግባባት ለመፍታት ዳገት ቢወጡ ቁልቁል ቢወርዱ ሊሳካ አልቻለም፤አሠልጣኞችም ነገሩ ከብዷቸው ሁለቱም ሴት አትሌቶች በተለያየ አሠልጣኝ የተለያየ ቦታ እንዲሠሩ እሰከማድረግ ደርሠዋል፤በውስጥ የተቋጠረው ቂም በሽማግሌም፣በገላጋይ አልፈታም ብሎ በመጨረሻም ድምዳሜው የአንደኛው ህይወት በአንደኛው እጅ መጥፋት ሆኗል።
♦️የአትሌቱ ህይወት ስላለፈበት አጋጣሚ
ገዳይ እንዴትና የት፣በምን ሁኔታ የሟችን ህይወት ነጠቀ የሚለው ብዙዎች ለማወቅና እርግጠኛ መሆን የሚፈልጉበት ጥያቄ ነው፤በገዳይነት የተጠረጠረው አትሌት ደረሠ ረታ በውስጡ በተፈጠረ አንዳች ስሜት ተነሳስቶ ወደ ሠንዳፋ የልምምድ ቦታ ድንገት አመራ፤በዛች ቀን የተደገሠለትን ድግስና ከሞት ጋር ቀጠሮ እንዳለው ለሠከንድም ቢሆን ያላሠበው የቀድሞ አትሌት ይሄይስ ታደለው ባለቤቱን አትሌት ወርቅነሽ ዓለሙን ከፊት ሆኖ እያሠራ እያለ በድንገት በተተኮሠበት ጥይት ይህቺን ዓለም ዳግም ላይመለስባት ለዘለዓለሙ አሸልቧል።በገዳይነት የተጠረጠረው ከፊቱ በርካታ የአትሌቲክስ የስኬት ዓመታት እንዳሉት የሚነገርለት በግድያ የተጠረጠረው አትሌት ደረሠ ረታ ከግድያው በኋላ ራሱን ለማሸሽ ጥረት ቢያደርግም በአካባቢው በነበሩ አርሶ አደሮች ጥረት ተይዞ አሁን ሠንዳፋ በሚገኘው ማረሚያ ቤት በህግ ጥላ ስር ውሎ ጉዳዩን እየተከታተለ ይገኛል።
♦️"በጣም ተፈታተነኝ፣በጣም ታገለኝ"የሚል አጭር ቃል የተነፈሠው ገዳይ
በግድያ ተጠርጥሮ በህግ ጥላ ስር የሚገኘው አትሌት ደረሠ ረታ ከግድያው በኋላ በተለይ ዛሬ ከሟች አትሌት ይሄይስ ታደለው የቀብር ስነ-ስርዓቱ ከተፈፀመ በኋላ የቅርብ ወዳጆቹ ለምን እንደዚህ አይነት ውሳኔ እንደወሠነ ጠይቀውት ከገጠመው ያልታሠበ ፈተና ውስጥ የወደቀው አትሌቱ በፀፀት ውስጥ ሆኖ "በጣም ተፈታተነኝ፣በጣም ታገለኝ"የሚል አጭር ቃል ከመናገር የዘለለ መተንፈስ እንዳልቻለ ለሀትሪክ ስፖርት ኦፊሺያል ገልፀዋል።
♦️የአትሌት ይሄይስ ታደለው የመጨረሻ ስንብት
የአትሌት ይሄይስ ታደለው የቀብር ስነ-ስርዓቱና የአስከሬን ሽኝት ዛሬ ከቀኑ በ6:00 በሚኖሩበት ሠንዳፋ በኬ ማርያም ቤተክርስቲያን የአትሌቱ ቤተሠቦች፣ጓደኞች፣አሠልጣኞች፣አትሌቶችና የስፖርት ቤተሠቦች በተገኙበት በክብር አርፏል።በጉዳት ምክንያት ከአትሌቲክስ ርቆ ባለቤቱን በማሠራት የሚያሳልፈው አትሌት ይሄይስ ታደለው እንደዋዛ ይህቺን ዓለምና አትሌቲክሱንም ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ተሠናብቷል።
♦️ለኢት.አ.ፌዴሬሽንና ለአትዮጵያ አትሌቶች ማህበር መልዕክት
የኢት.አ.ፌዴሬሽንና የአትዮጵያ አትሌቶች ማህበር እስከአሁን በአሳዛኙ ክስተት ዙሪያ የተነፈሱት ነገር አለመኖሩ ትዝብትን ፈጥሯል፤እንደ ሀገርም እንደ አትሌቲክሱ ዓለምም ትልቅ ስብራትና ልብ ሠባሪ አጋጣሚ ነው፤ሁለቱም አካላት በአትሌቶቹ መካከል የተፈጠረውን ግድያ ወደ ሌሎች እንዳይዛመትና በዚሁ እንዲያበቃ በይፋ በመግለጫ ጭምር ማውገዝና ማስተማር ይጠበቅባቸዋል።ከዚህ በፊት በተመሳሳይ ምክንያቶች የጠፋውን ውዱን የሠው ልጅ ህይወት መለስ ብሎ ላስታወሠ በጎረቤት ኬንያ በጥይት አረር ህይወታቸው የተነጠቁ አትሌቶች፣አሠልጣኞችና የአትሌቶች ህይወት እንደዋዛ መነጠቁን በትዝታ ፈረስ ወደኋላ ሄዶ ላስታወሠ ጉዳዩ ቢያሳስበው አይፈረድበትም፤ይሄ በአትሌቶች መካከል ያለውን የአጉል ባህልና ዕምነት፣የመጠራጠርና የመጠፋፋት ባህል እንደወረርሽኝ ተዛምቶ ለተጨማሪ አደጋ ከመጋለጣችን በአሠልጣኞችና በአትሌቶች አእምሮ ላይ ስራ ይሠራ።
3 days ago
የአርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ሥርዓተ ቀብር ተፈጸመ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 25፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ሁለገብ የጥበብ ሰው አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ሥርዓተ ቀብር በዛሬው ዕለት በአዲስ አበባ አማኑኤል ቤተክርስቲያን ተፈጽሟል።
አርቲስት ኪዳኔ ባጋጠመው ህመም በህክምና ሲረዳ ቆይቶ ግንቦት 23 ቀን 2018 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት የተለየ ሲሆን÷ ሥርዓተ ቀብሩ ቤተሰቦቹ፣ ጓደኞቹ፣ የሙያ አጋሮቹና አድናቂዎቹ በተገኙበት ነው የተፈጸመው።
አርቲስቱ በሙያው ባገለገለበት ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት ከጠዋቱ 3:00 ሰዓት ጀምሮ የሽኝትና ሻማ የማብራት ሥነ ሥርዓት ተካሂዷል።
ለተለያዩ የቴሌቪዥን ዝግጅቶችና የበዓል ፕሮግራሞች ላይ ባቀረባቸው የጥበብ ስራዎች ድምቀት የነበረው አርቲስት ኪዳኔ÷ በፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን ፋና 80 የውዝዋዜ እና የዳንስ ተሰጥኦ ውድድር ላይ በአማካሪነት በመስራት ሙያዊ አስተዋጽዖ አበርክቷል።
ሁለገቡ ከያኒ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ከ2017 ዓ.ም ጀምሮ ህይወቱ እስካለፈበት ቀን ድረስ በአንጋፋው ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት ተዘዋውሮ በሙያው ሀገሩን እና ወገኑን በታማኝነትና በትጋት አገልግሏል።
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 25፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ሁለገብ የጥበብ ሰው አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ሥርዓተ ቀብር በዛሬው ዕለት በአዲስ አበባ አማኑኤል ቤተክርስቲያን ተፈጽሟል።
አርቲስት ኪዳኔ ባጋጠመው ህመም በህክምና ሲረዳ ቆይቶ ግንቦት 23 ቀን 2018 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት የተለየ ሲሆን÷ ሥርዓተ ቀብሩ ቤተሰቦቹ፣ ጓደኞቹ፣ የሙያ አጋሮቹና አድናቂዎቹ በተገኙበት ነው የተፈጸመው።
አርቲስቱ በሙያው ባገለገለበት ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት ከጠዋቱ 3:00 ሰዓት ጀምሮ የሽኝትና ሻማ የማብራት ሥነ ሥርዓት ተካሂዷል።
ለተለያዩ የቴሌቪዥን ዝግጅቶችና የበዓል ፕሮግራሞች ላይ ባቀረባቸው የጥበብ ስራዎች ድምቀት የነበረው አርቲስት ኪዳኔ÷ በፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን ፋና 80 የውዝዋዜ እና የዳንስ ተሰጥኦ ውድድር ላይ በአማካሪነት በመስራት ሙያዊ አስተዋጽዖ አበርክቷል።
ሁለገቡ ከያኒ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ከ2017 ዓ.ም ጀምሮ ህይወቱ እስካለፈበት ቀን ድረስ በአንጋፋው ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት ተዘዋውሮ በሙያው ሀገሩን እና ወገኑን በታማኝነትና በትጋት አገልግሏል።
3 days ago
ተፈጸመ
#ethiopia | በተለያዩ የጥበብ ዘርፎች በስፋት የሚታወቀው አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ባደረበት ህመም በህክምና ሲረዳ ቆይቶ ግንቦት 23 ቀን 2018 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል።
የአርቲስቱ የቀብር ስነ ስርዓት ዛሬ፣ ማክሰኞ ግንቦት 25 ቀን 2018 ዓ.ም በደብረ ገሊላ ቅዱስ አማኑኤል ካቴድራል ( አማኑኤል አጂፕ ) ከቀኑ 6:00 ሰዓት ተፈጽሟል።
ከጠዋቱ 3:00 ሰዓት ጀምሮ በሙያ ህይወቱ በታማኝነት ባገለገለበት ታሪካዊው ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት የሽኝት እና የሻማ ማብራት መርሃ ግብር ተከናወናል።
***
የሁለገቡ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው
አጭር የህይወት ታሪክ
የመድረኩ እንዝርት ሁለገቡ የጥበብ ሰው አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ከእናቱ ከወ/ሮ ብዙነሽ ጓንጉል እና ከአባቱ ከአቶ ምስጋናው ደርኬሮ ሰኔ 15/ 1958 ዓ.ም አዲስ አበባ ከተማ ልዩ ስሙ አማኑኤል አጂፕ ተብሎ በሚጠራዉ አካባቢ ተወለደ፡፡ ለአቅመ ፊደል ሲደርስ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርቱን በደጃዝማች ኃይሉ ተስፋዬ ትምህርት ቤት እንዲሁም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱን በአዲስ ከተማ ትምሀርት ቤት እስከ 12ኛ ክፍል ተምሮ አጠናቋል።
ከውዝዋዜ ጋር ገና ተማሪ እያለ የተወዳጀው ሁለገቡ ከያኒ ኪዳኔ ምስጋናው የጥበብ ጉዞውን በቀበሌ ኪነትና በከፍተኛ ኪነት ውስጥ አድርጎ መዳረሻውን በአዲስ አበባ ቴአትርና ባህል አዳራሽ በማድረግ በ1977 ዓ.ም በውዝዋዜ ሙያ ለመቀጠር በቅቷል፡፡ የአርቲስት ኪዳኔ የሙያ ፍቅር፣ ችሎታና ስነምግባር ያስደመማቸው የውዝዋዜ ክፍል አሰልጣኞችና ኃላፊዎች ከተወዛዋዥነት ወደ ረዳት አሰልጣኝነት እንዲያድግ በማድረጋቸው ከ1983-1990 ዓ.ም ድረስ በረዳት አሰልጣኝነት ሙያ ሲያገለግል ቆይቷል፡፡ ጥበበኛው ኪዳኒ በረዳትነት የጀመረውን የአሰልጣኝነት ስራውን ከፍ በማድረግ ከ1991 እሰከ 1992 በቋሚ አሰልጣኝነት ተመድቦ በርካታ ባለሙያዎችን በክህሎት፣ በስነምግባርና በጥበብ አሰልጥኖ ለውዝዋዜ ሙያ መስፋፋትና አድገት የበኩሉን ድርሻ አበርክቷል፡፡
በውዝዋዜ ጥበብ በማለዳው የተነደፈው ኪዳኔ በእውቀት፣ በልምድና በፈጠራ እየጎመራና አንቱታን እያተረፈ ሲመጣ አድማሱን በማስፋት በአንጋፋው ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት ተዛውሮ ከ1992 እሰከ 2007 ዓ.ም በዋና አሰልጣኝነትና በኬሮጋራፈርነት በርካታ በሀገር አቀፍና በአለም አቀፍ ደረጃ ግዘፍ የነሱ መድረኮች ላይ የቀረቡ የውዝዋዜ ስራዎችን በማዘጋጀት፣ በማማከርና በመምራት ከሰው ልብና አእምሮ የማይጠፉ ደማቅ ኪነጥበባዊ ስራዎችን ሰርቷል፡፡
አርቲስት ኪዳኔ ፈጣን የፈጠራ፣ የማደራጀትና የመምራት አቅም የነበረው ብርቱ የጥበብ ሰው ነበር፡፡ በርካታ ተወዛዋዦች የሚገኙበት የጥበብ መድረክ ካለ እዛ የጥበብ መድረክ ላይ ኪዳኔ መኖሩ ሳይታለም የተፈታ ህልም ነበር፡፡ የኪዳኔ የፈጠራ፣ የውዝዋዜ ችሎታና የውዝዋዜ ዝግጅት ጥበብ የታየባቸው አያሌ የውዝዋዜ ጥበብ ስራዎች ህያው መስክሮቹ ናቸው፡፡ በፋሽስት ጣሊያን የተዘረፈው የአክሱም ሀውልት ወደ ሀገሩ ሲመለስ ለነበረው አቀባበል በተዘጋጀው የኪነጥበብ መድረክ ላይ በአዲስ አበባና በአክሱም ከተማ ግዙፍ የውዝዋዜ ዝግጅት፣ በህዳሴ ግድብ ማስተባበሪያ በተዘጋጀው የጥበብ መድረክ፣ በሚሊኒዬም አዳራሽ፣ በባህዳር ጣና ሐይቅ ላይ የውዝዋዜ የጀልባ ላይ ትርኢት፣ የአዲስ ዓመት የበዓል ዝግጅቶች ላይ ጥበብ፣ ባህል፣ ፈጠራና ውበት የተመላባቸው በርካታ ተወዛዋዦች የተሳተፉባቸውን የጥበብ ስራዎች በማዘጋጀት የጥበብና የሀገር ባለውለታነቱን አስመስክሯል፡፡
በአንጋፋው ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት ከአስራ አምስት ዓመት በላይ በአሰልጣኝነት ሲሰራ ከቆየ በኋላ ከ2007 እስከ 2017 ዓ.ም ድረስ ወደ ቀድሞ የሙያ ቤቱ የአዲስ አበባ ቴአትርና ባህል አደራሽ ተዛውሮ በአሰልጣኝነትና በኬሮግራፈርነት ሲሰራ ቆይቷል፡፡
አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ከተወዛዋዠነት፣ አሰልጣኝነት፣ አዘጋጅነትና አማካሪነት ባሻገር በድምጻዊነትና በቴአትርና ፊልም ተዋናይነትም በመሳተፍ ሁለገብ ከያኒነቱን ያስመሰከረ ድንቅ ጥበበኛ ነበር፡፡ በርካታ የሙዚቃ ቪዲዮ ስራዎች ላይ የኪዳኔ ደማቅ የፈጠራና የጥበብ አሻራ ያረፈባቸው ውዝዋዜዎችና ዝግጅቶች ዛሬም፣ ነገም ህያው ምስክሮች ናቸው፡፡
አሰልጣኝና ኬሮግራፍር እንዲሁም የውዝዋዜ አማካሪ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው በሞያው በሰራባቸው አመታት በርካታ
1. ባለሙያዎች ወደ ሙያው እንዲገቡና የሙያው ስነምግባር እንዲኖራቸው አደርጓል፡፡
2. የባህል ውዝዋዜ ትምህርት ቤት በሌለበት ዘመን በቴአትር ቤቶችና ከቴአትር ቤቶች ውጪ የነበሩ ወጣቶችን አሰልጥናል፤
3. ከከተማ ውጪ በመሄድ ቱባ ባህሎችን በማጥናትና በማምጣት የተለያዩ የባህል ጭፈራዎችንና አለባበሶችን አስተዋውቋል፡፡
4. የውዝዋዜ ሙያ እንደሙያ እንዲታይና አሁን የደረሰበት ደረጃ ላይ እንዲደርስ የተለያዩ መድረኮች ላይ እና ጥናቶች ላይ በመሳተፍ አስተዋኦ አበርክቷል፡፡
5. በአዲስ አበባ ከተማ በተዘጋጁ በርካታ የኪነ ጥበብ ፌስቲቫሎች ላይ በመጋበዝ በዳኝነትና በአማካሪነት ሰርቷል፡፡
6. ከአዲስ አበባ ውጪ በተለያዩ ክልሎች የሚገኙ ወጣቶችን ከማሰልጠን አልፎ በደቡብ ክልል ውስጥ የባህል ባንድ ለማቋቋም በቅቷል፡፡
7. በከተማችንና በተለያዩ ከተሞች በተከበሩ የብሄሔር ብሄረሰቦች ክብረ በዓላት ላይ የጥበብ ስራዎችን አቅርባል፡፡
8. በተለያዩ ጊዜ የተከበሩ የአደባበይ በአላት አድዋና የካቲት12 የመሳሰሉት ላይ ስራዋችን አቅርባል፡፡
9. በታላቁ ህዳሴ ግድብ ድረስ በመሄድና ታስቦ በሚከበርበት ጊዜም ስራዎችን አቅርቧል፡፡
10. በመንግስት መስረታና በበአለ ሲመቱ ዝግጅት ላይ ታላቅ የውዝዋዜ ትርኢት በኬሮግራፈርነት ሰርቷል፡፡
11. ሀገራችን የጦርነትና የተፈጥሮ ችግር በገጠማት ጊዜ ከኪነ ጥበብ ስራው ጋር ቀዳሚ በመሆን በርካታ አነቃቂ ስራዎችን ሰርቷል፡፡
12. የተለያዩ የሀገር መሪዎች፣ አንባሳደሮችና ዲፕሎማቶች ሲመጡና ሲሸኙ በአየር መንገድና በከንቲባ ጽ/ቤት ግቢ ውስጥ ደማቅ አቀባበል በማደረግ እና ትርኢቶችን በማቅረብ ባህላችንን አስተዋውቋል፡፡
13. በከተማ ደረጃ የሚዘጋጁ ትላልቅ ሴሚናሮች፤ጉባኤዋችና ሲንፖዚየሞች ላይ የተለያዩ የኬሮግራፈር ስራዎችን ሰርቷል፡፡
ሁለገቡ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ላበረከታቸው ኪነጥበባዊ ስራዎች የምስጋናና የእውቅና የምስክር ወረቀቶችን፡-
Ø ከኢፌድሪ ፊዴሬሽን ምክር ቤት
Ø ከኢፌድሪ ባህልና ቱሪዝም ሚንስቴር
Ø አዲስ አበባ ዩንቪርስቲ
Ø ከአዲስ አበባ ባህል ኪነ የጥበብና ቱሪዝም ቢሮ
Ø ከታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ማስተባበሪያ ጽ/ቤት
Ø ከሀገር ፍቅር፤ከቴአትርና ባህል አደራሽ፤ከራስ ቴአትር፤ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአተር እና ሌሎችም በርካታ ተቋማት በክብር ተቀብሏል፡፡
አሰልጣኝ፣ ኬሮግራፍርና የውዝዋዜ አማካሪ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ሙያው እንዲያድግና ባለሙያውም እንዲጠቀም በነበረው ፍላጎትና ቁጭት ምክንያት ሙያው በተለያዩ ትልልቅ ሆቴሎችና የባህል ምሽቶች እንዲሰራና ባህላችን የበለጠ እንዲተዋወቅ በማማከርና በመደገፍ የአንበሳውን ድርሻ ይወስዳል፡፡
አርቲስት ኪዳኔ ከበርካታ የሀገራችን ታዋቂና ተወዳጅ ሙዚቀኞች ጋር ትላልቅ መድረኮችና በከተማ ደረጃ በቀረቡ ታላላቅ ህዝባዊ በአላትና የሙዚቃ ኮንሰርቶች ላይ የኪሮግራፈር ስራዋችን
Ø በሸራተን አዲስ ሆቴል
Ø በሚሊንየም አዳራሽ
Ø በኢግዚብሽን ማዕከል
Ø በመስቀል አደባባይ
Ø በአዲስ አበባ ስቴድየም
Ø በጊዮን ሆቴል
Ø በሂልተን ሆቴል
Ø በስካይላት ሆቴል በመገኘት ጥበባዊ ስራዎችን ያቀረበ ሲሆን ትልልቅ የቀጥታ የቴሌብዥን ስርጭ የነበራቸውን ግዙፍ መድረኮችም ላይ ልዩ የኬሮግራፈርነት ሙያውን ድንቅ ብቃት አስመስክሯል፡፡
አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው በተለያዩ ቴአትርና ሙዚቃዊ ቴአትሮች ላይ በትወናና በዝግጅት ሰርቷል፡፡ በትወና የተሳተፈባቸው ስራዎች፦
Ø ጤና ያጣ ፍቅር
Ø ሮሚዮና ጁሌት
Ø የቀለጠው መንድር
Ø ሊስትሮ ኦፔራ
Ø ከልሺን አውልቂ
Ø ፎርፌ
Ø ኦቴሎ
Ø ቴዎድሮስ
በሙዚቃዊ ድራማ ኬሮግራፈር ዝግጅት፡-
Ø ፎርፌ
Ø ኢትዮጵያዊነት ጥልቅ ነው
Ø ከልሽን አውልቂ
Ø ሊስትሮ ኦፔራ
Ø ሉሲ
Ø ሀገር ማለት ሰው ነው እና ሌሎችም የጠቀሳሉ፡፡
በፊልም ትወና፡-
Ø በህይወት ዙሪያ
Ø ሔሮሽማ
አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ከመድረክ ስራዎቹ በተጨማሪም በተላያዩ ታዋቂና አንጋፍ እንዲሁም ወጣት ድምጻውያን የሙዚቃ ቪዲዮ ስራዎች ላይ በኬሮግራፈርነትና በአማካሪነት ሰርቷል፡፡
Ø ለክብር ዳ/ር ጥላሁን ገሠሠ
Ø ለድምፃዊ ኤፍሬም ታምሩ የሰራቸው ስራዎች ጥቂቶቹ ናቸው፡፡
አርቲስት ኪዳኔ በተለያዩ የቴሌቪዥን ዝግጅቶችና የበዓል ፕሮግራሞች ላይ ባቀረባቸው የጥበብ ስራዎች ውበትና ድምቀት የነበረ ሲሆን በፋና ቴሌቭዥን ፋና ሰማንያ የውዝዋዜና ዳንስ ተሰጥኦ ውድድር ላይ በአማካሪነት በመስራት ሙያዊ አስተዋፅዎ አድርጓል፡፡
ሁለገቡ አርቲስት ኪዳኔ በሙያው አድማስ ተሸግሮ በዱባይ እና በታይላንድ ኢትዮጰያንና ባህሏን ያስተዋወቀ ብርቱ የጥበብ ሰው ሰሆን በቅርብ በሀገራችን እና በአለም ህዝቦች ዘንድ አንድ ጊዜ ተሰርቶ ያልተደገመውን የህዝብ ለህዝብ ተጓዥ የሙዚቃ የባህል ቡድንን የሚያስታውስ የሀገረሰብ ሙዚቃዎችን፣ ጭፈራዎችንና ባህላችንን የሚያስተዋውቅ ሉሲ ድንቅነሽ ኢትዮጵያ በሚል በመላው ሀገር ተዟዙሮ የቀረበውን ትርኢት ከባህል ሚንስቴር ኃላፊነት ተሰጥቶት በዋና አዘጋጅነት የውዝዋዜውን ዝግጅት መምራት የቻለ ድንቅ ጥበበኛ ነበር፡፡
ሁለገቡ ከያኒ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ከ2017 ዓ.ም ጀምሮ ህይወቱ እስካለፈበት ግንቦት 23/2018 ዓ.ም ድረስ በአንጋፋው ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት ተዛውሮ በሙያው ወገኑን፣ ሀገሩንና ሙያውን በጥበብ፣ በታማኝነትና በትጋት ሲያገለግል የኖረ፣ በጥበብ ስራዎቹ ስሙን ከመቃብር በላይ ማኖር የቻለ ታላቅ ጥበበኛ ነበር፡፡
አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናዉ የጋብቻ ህይወቱን ከረዥም ጊዜ ፍቅረኛዉ ከወ/ት አይናለም ተፈራ ጋር የካቲት 2 /2018 በክብር ፈፅሟል። ይሁንና ይህ ታላቅ ጥበበኛ ባጋጠመው የጤና እክል ሳቢያ በአዲስ ህይወት አጠቃላይ ሆስፒታል እና በሆፕ ሆስፒታል በህክምና ሲረዳ ቆይቶ ግንቦት 23/2018 ዓ.ም በተወለደ በ60 ዓመቱ ከዚህ ዓለም ድካም አርፏል፡፡
የአርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው የሽኝትና የጧፍ ማብራት ፕሮግራም ቤተሰቦቹ፣ ጓደኞቹ፣ የሙያ አጋሮቹና አድናቂዎቹ በተገኙበት ለረዥም ዓመታት በሙያው ባገለገለበት አንጋፋው ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት ግንቦት 25/ 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ በ3፡00 ሰዓት ላይ ከተከናወነ በኋላ የቀብር ሰነ ስርዓቱ በአማኑኤል ካቴድራል ቤተክርስቲያን ይፈፀማል።
የአዲስ አበባ ቴአትር ቤቶች አስተዳደር ድርጅት በመላው ሰራተኞቹና የሙያ አጋሮቹ ስም በሁለገቡ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ህልፈተ ህይወት የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን እየገለፀ ፈጣሪ ነፍሱን በመዓዛ ገነት እንዲያሳርፍ ይመኛል፡፡ እንዲሁም ለውድ ቤተሰቦቹ፣ ለዘመዶቹ፣ ለጓደኞቹ፣ ለስራ ባልደረቦቹ፣ ለሙያ አጋሮቹና አድናቂዎቹ በሙሉ ፈጣሪ ልባዊ መጽናናትን እንዲሰጣቸው ይመኛል፡፡
የአዲስ አበባ ቴአትር ቤቶች አስተዳደር ድርጅት-ኮምኒኬሽን
#ኪዳኔምስጋናው #ሀገርፍቅርቴአትር #የጥበብሰው #ሀዘን #ኪነጥበብ #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | በተለያዩ የጥበብ ዘርፎች በስፋት የሚታወቀው አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ባደረበት ህመም በህክምና ሲረዳ ቆይቶ ግንቦት 23 ቀን 2018 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል።
የአርቲስቱ የቀብር ስነ ስርዓት ዛሬ፣ ማክሰኞ ግንቦት 25 ቀን 2018 ዓ.ም በደብረ ገሊላ ቅዱስ አማኑኤል ካቴድራል ( አማኑኤል አጂፕ ) ከቀኑ 6:00 ሰዓት ተፈጽሟል።
ከጠዋቱ 3:00 ሰዓት ጀምሮ በሙያ ህይወቱ በታማኝነት ባገለገለበት ታሪካዊው ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት የሽኝት እና የሻማ ማብራት መርሃ ግብር ተከናወናል።
***
የሁለገቡ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው
አጭር የህይወት ታሪክ
የመድረኩ እንዝርት ሁለገቡ የጥበብ ሰው አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ከእናቱ ከወ/ሮ ብዙነሽ ጓንጉል እና ከአባቱ ከአቶ ምስጋናው ደርኬሮ ሰኔ 15/ 1958 ዓ.ም አዲስ አበባ ከተማ ልዩ ስሙ አማኑኤል አጂፕ ተብሎ በሚጠራዉ አካባቢ ተወለደ፡፡ ለአቅመ ፊደል ሲደርስ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርቱን በደጃዝማች ኃይሉ ተስፋዬ ትምህርት ቤት እንዲሁም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱን በአዲስ ከተማ ትምሀርት ቤት እስከ 12ኛ ክፍል ተምሮ አጠናቋል።
ከውዝዋዜ ጋር ገና ተማሪ እያለ የተወዳጀው ሁለገቡ ከያኒ ኪዳኔ ምስጋናው የጥበብ ጉዞውን በቀበሌ ኪነትና በከፍተኛ ኪነት ውስጥ አድርጎ መዳረሻውን በአዲስ አበባ ቴአትርና ባህል አዳራሽ በማድረግ በ1977 ዓ.ም በውዝዋዜ ሙያ ለመቀጠር በቅቷል፡፡ የአርቲስት ኪዳኔ የሙያ ፍቅር፣ ችሎታና ስነምግባር ያስደመማቸው የውዝዋዜ ክፍል አሰልጣኞችና ኃላፊዎች ከተወዛዋዥነት ወደ ረዳት አሰልጣኝነት እንዲያድግ በማድረጋቸው ከ1983-1990 ዓ.ም ድረስ በረዳት አሰልጣኝነት ሙያ ሲያገለግል ቆይቷል፡፡ ጥበበኛው ኪዳኒ በረዳትነት የጀመረውን የአሰልጣኝነት ስራውን ከፍ በማድረግ ከ1991 እሰከ 1992 በቋሚ አሰልጣኝነት ተመድቦ በርካታ ባለሙያዎችን በክህሎት፣ በስነምግባርና በጥበብ አሰልጥኖ ለውዝዋዜ ሙያ መስፋፋትና አድገት የበኩሉን ድርሻ አበርክቷል፡፡
በውዝዋዜ ጥበብ በማለዳው የተነደፈው ኪዳኔ በእውቀት፣ በልምድና በፈጠራ እየጎመራና አንቱታን እያተረፈ ሲመጣ አድማሱን በማስፋት በአንጋፋው ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት ተዛውሮ ከ1992 እሰከ 2007 ዓ.ም በዋና አሰልጣኝነትና በኬሮጋራፈርነት በርካታ በሀገር አቀፍና በአለም አቀፍ ደረጃ ግዘፍ የነሱ መድረኮች ላይ የቀረቡ የውዝዋዜ ስራዎችን በማዘጋጀት፣ በማማከርና በመምራት ከሰው ልብና አእምሮ የማይጠፉ ደማቅ ኪነጥበባዊ ስራዎችን ሰርቷል፡፡
አርቲስት ኪዳኔ ፈጣን የፈጠራ፣ የማደራጀትና የመምራት አቅም የነበረው ብርቱ የጥበብ ሰው ነበር፡፡ በርካታ ተወዛዋዦች የሚገኙበት የጥበብ መድረክ ካለ እዛ የጥበብ መድረክ ላይ ኪዳኔ መኖሩ ሳይታለም የተፈታ ህልም ነበር፡፡ የኪዳኔ የፈጠራ፣ የውዝዋዜ ችሎታና የውዝዋዜ ዝግጅት ጥበብ የታየባቸው አያሌ የውዝዋዜ ጥበብ ስራዎች ህያው መስክሮቹ ናቸው፡፡ በፋሽስት ጣሊያን የተዘረፈው የአክሱም ሀውልት ወደ ሀገሩ ሲመለስ ለነበረው አቀባበል በተዘጋጀው የኪነጥበብ መድረክ ላይ በአዲስ አበባና በአክሱም ከተማ ግዙፍ የውዝዋዜ ዝግጅት፣ በህዳሴ ግድብ ማስተባበሪያ በተዘጋጀው የጥበብ መድረክ፣ በሚሊኒዬም አዳራሽ፣ በባህዳር ጣና ሐይቅ ላይ የውዝዋዜ የጀልባ ላይ ትርኢት፣ የአዲስ ዓመት የበዓል ዝግጅቶች ላይ ጥበብ፣ ባህል፣ ፈጠራና ውበት የተመላባቸው በርካታ ተወዛዋዦች የተሳተፉባቸውን የጥበብ ስራዎች በማዘጋጀት የጥበብና የሀገር ባለውለታነቱን አስመስክሯል፡፡
በአንጋፋው ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት ከአስራ አምስት ዓመት በላይ በአሰልጣኝነት ሲሰራ ከቆየ በኋላ ከ2007 እስከ 2017 ዓ.ም ድረስ ወደ ቀድሞ የሙያ ቤቱ የአዲስ አበባ ቴአትርና ባህል አደራሽ ተዛውሮ በአሰልጣኝነትና በኬሮግራፈርነት ሲሰራ ቆይቷል፡፡
አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ከተወዛዋዠነት፣ አሰልጣኝነት፣ አዘጋጅነትና አማካሪነት ባሻገር በድምጻዊነትና በቴአትርና ፊልም ተዋናይነትም በመሳተፍ ሁለገብ ከያኒነቱን ያስመሰከረ ድንቅ ጥበበኛ ነበር፡፡ በርካታ የሙዚቃ ቪዲዮ ስራዎች ላይ የኪዳኔ ደማቅ የፈጠራና የጥበብ አሻራ ያረፈባቸው ውዝዋዜዎችና ዝግጅቶች ዛሬም፣ ነገም ህያው ምስክሮች ናቸው፡፡
አሰልጣኝና ኬሮግራፍር እንዲሁም የውዝዋዜ አማካሪ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው በሞያው በሰራባቸው አመታት በርካታ
1. ባለሙያዎች ወደ ሙያው እንዲገቡና የሙያው ስነምግባር እንዲኖራቸው አደርጓል፡፡
2. የባህል ውዝዋዜ ትምህርት ቤት በሌለበት ዘመን በቴአትር ቤቶችና ከቴአትር ቤቶች ውጪ የነበሩ ወጣቶችን አሰልጥናል፤
3. ከከተማ ውጪ በመሄድ ቱባ ባህሎችን በማጥናትና በማምጣት የተለያዩ የባህል ጭፈራዎችንና አለባበሶችን አስተዋውቋል፡፡
4. የውዝዋዜ ሙያ እንደሙያ እንዲታይና አሁን የደረሰበት ደረጃ ላይ እንዲደርስ የተለያዩ መድረኮች ላይ እና ጥናቶች ላይ በመሳተፍ አስተዋኦ አበርክቷል፡፡
5. በአዲስ አበባ ከተማ በተዘጋጁ በርካታ የኪነ ጥበብ ፌስቲቫሎች ላይ በመጋበዝ በዳኝነትና በአማካሪነት ሰርቷል፡፡
6. ከአዲስ አበባ ውጪ በተለያዩ ክልሎች የሚገኙ ወጣቶችን ከማሰልጠን አልፎ በደቡብ ክልል ውስጥ የባህል ባንድ ለማቋቋም በቅቷል፡፡
7. በከተማችንና በተለያዩ ከተሞች በተከበሩ የብሄሔር ብሄረሰቦች ክብረ በዓላት ላይ የጥበብ ስራዎችን አቅርባል፡፡
8. በተለያዩ ጊዜ የተከበሩ የአደባበይ በአላት አድዋና የካቲት12 የመሳሰሉት ላይ ስራዋችን አቅርባል፡፡
9. በታላቁ ህዳሴ ግድብ ድረስ በመሄድና ታስቦ በሚከበርበት ጊዜም ስራዎችን አቅርቧል፡፡
10. በመንግስት መስረታና በበአለ ሲመቱ ዝግጅት ላይ ታላቅ የውዝዋዜ ትርኢት በኬሮግራፈርነት ሰርቷል፡፡
11. ሀገራችን የጦርነትና የተፈጥሮ ችግር በገጠማት ጊዜ ከኪነ ጥበብ ስራው ጋር ቀዳሚ በመሆን በርካታ አነቃቂ ስራዎችን ሰርቷል፡፡
12. የተለያዩ የሀገር መሪዎች፣ አንባሳደሮችና ዲፕሎማቶች ሲመጡና ሲሸኙ በአየር መንገድና በከንቲባ ጽ/ቤት ግቢ ውስጥ ደማቅ አቀባበል በማደረግ እና ትርኢቶችን በማቅረብ ባህላችንን አስተዋውቋል፡፡
13. በከተማ ደረጃ የሚዘጋጁ ትላልቅ ሴሚናሮች፤ጉባኤዋችና ሲንፖዚየሞች ላይ የተለያዩ የኬሮግራፈር ስራዎችን ሰርቷል፡፡
ሁለገቡ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ላበረከታቸው ኪነጥበባዊ ስራዎች የምስጋናና የእውቅና የምስክር ወረቀቶችን፡-
Ø ከኢፌድሪ ፊዴሬሽን ምክር ቤት
Ø ከኢፌድሪ ባህልና ቱሪዝም ሚንስቴር
Ø አዲስ አበባ ዩንቪርስቲ
Ø ከአዲስ አበባ ባህል ኪነ የጥበብና ቱሪዝም ቢሮ
Ø ከታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ማስተባበሪያ ጽ/ቤት
Ø ከሀገር ፍቅር፤ከቴአትርና ባህል አደራሽ፤ከራስ ቴአትር፤ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአተር እና ሌሎችም በርካታ ተቋማት በክብር ተቀብሏል፡፡
አሰልጣኝ፣ ኬሮግራፍርና የውዝዋዜ አማካሪ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ሙያው እንዲያድግና ባለሙያውም እንዲጠቀም በነበረው ፍላጎትና ቁጭት ምክንያት ሙያው በተለያዩ ትልልቅ ሆቴሎችና የባህል ምሽቶች እንዲሰራና ባህላችን የበለጠ እንዲተዋወቅ በማማከርና በመደገፍ የአንበሳውን ድርሻ ይወስዳል፡፡
አርቲስት ኪዳኔ ከበርካታ የሀገራችን ታዋቂና ተወዳጅ ሙዚቀኞች ጋር ትላልቅ መድረኮችና በከተማ ደረጃ በቀረቡ ታላላቅ ህዝባዊ በአላትና የሙዚቃ ኮንሰርቶች ላይ የኪሮግራፈር ስራዋችን
Ø በሸራተን አዲስ ሆቴል
Ø በሚሊንየም አዳራሽ
Ø በኢግዚብሽን ማዕከል
Ø በመስቀል አደባባይ
Ø በአዲስ አበባ ስቴድየም
Ø በጊዮን ሆቴል
Ø በሂልተን ሆቴል
Ø በስካይላት ሆቴል በመገኘት ጥበባዊ ስራዎችን ያቀረበ ሲሆን ትልልቅ የቀጥታ የቴሌብዥን ስርጭ የነበራቸውን ግዙፍ መድረኮችም ላይ ልዩ የኬሮግራፈርነት ሙያውን ድንቅ ብቃት አስመስክሯል፡፡
አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው በተለያዩ ቴአትርና ሙዚቃዊ ቴአትሮች ላይ በትወናና በዝግጅት ሰርቷል፡፡ በትወና የተሳተፈባቸው ስራዎች፦
Ø ጤና ያጣ ፍቅር
Ø ሮሚዮና ጁሌት
Ø የቀለጠው መንድር
Ø ሊስትሮ ኦፔራ
Ø ከልሺን አውልቂ
Ø ፎርፌ
Ø ኦቴሎ
Ø ቴዎድሮስ
በሙዚቃዊ ድራማ ኬሮግራፈር ዝግጅት፡-
Ø ፎርፌ
Ø ኢትዮጵያዊነት ጥልቅ ነው
Ø ከልሽን አውልቂ
Ø ሊስትሮ ኦፔራ
Ø ሉሲ
Ø ሀገር ማለት ሰው ነው እና ሌሎችም የጠቀሳሉ፡፡
በፊልም ትወና፡-
Ø በህይወት ዙሪያ
Ø ሔሮሽማ
አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ከመድረክ ስራዎቹ በተጨማሪም በተላያዩ ታዋቂና አንጋፍ እንዲሁም ወጣት ድምጻውያን የሙዚቃ ቪዲዮ ስራዎች ላይ በኬሮግራፈርነትና በአማካሪነት ሰርቷል፡፡
Ø ለክብር ዳ/ር ጥላሁን ገሠሠ
Ø ለድምፃዊ ኤፍሬም ታምሩ የሰራቸው ስራዎች ጥቂቶቹ ናቸው፡፡
አርቲስት ኪዳኔ በተለያዩ የቴሌቪዥን ዝግጅቶችና የበዓል ፕሮግራሞች ላይ ባቀረባቸው የጥበብ ስራዎች ውበትና ድምቀት የነበረ ሲሆን በፋና ቴሌቭዥን ፋና ሰማንያ የውዝዋዜና ዳንስ ተሰጥኦ ውድድር ላይ በአማካሪነት በመስራት ሙያዊ አስተዋፅዎ አድርጓል፡፡
ሁለገቡ አርቲስት ኪዳኔ በሙያው አድማስ ተሸግሮ በዱባይ እና በታይላንድ ኢትዮጰያንና ባህሏን ያስተዋወቀ ብርቱ የጥበብ ሰው ሰሆን በቅርብ በሀገራችን እና በአለም ህዝቦች ዘንድ አንድ ጊዜ ተሰርቶ ያልተደገመውን የህዝብ ለህዝብ ተጓዥ የሙዚቃ የባህል ቡድንን የሚያስታውስ የሀገረሰብ ሙዚቃዎችን፣ ጭፈራዎችንና ባህላችንን የሚያስተዋውቅ ሉሲ ድንቅነሽ ኢትዮጵያ በሚል በመላው ሀገር ተዟዙሮ የቀረበውን ትርኢት ከባህል ሚንስቴር ኃላፊነት ተሰጥቶት በዋና አዘጋጅነት የውዝዋዜውን ዝግጅት መምራት የቻለ ድንቅ ጥበበኛ ነበር፡፡
ሁለገቡ ከያኒ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ከ2017 ዓ.ም ጀምሮ ህይወቱ እስካለፈበት ግንቦት 23/2018 ዓ.ም ድረስ በአንጋፋው ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት ተዛውሮ በሙያው ወገኑን፣ ሀገሩንና ሙያውን በጥበብ፣ በታማኝነትና በትጋት ሲያገለግል የኖረ፣ በጥበብ ስራዎቹ ስሙን ከመቃብር በላይ ማኖር የቻለ ታላቅ ጥበበኛ ነበር፡፡
አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናዉ የጋብቻ ህይወቱን ከረዥም ጊዜ ፍቅረኛዉ ከወ/ት አይናለም ተፈራ ጋር የካቲት 2 /2018 በክብር ፈፅሟል። ይሁንና ይህ ታላቅ ጥበበኛ ባጋጠመው የጤና እክል ሳቢያ በአዲስ ህይወት አጠቃላይ ሆስፒታል እና በሆፕ ሆስፒታል በህክምና ሲረዳ ቆይቶ ግንቦት 23/2018 ዓ.ም በተወለደ በ60 ዓመቱ ከዚህ ዓለም ድካም አርፏል፡፡
የአርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው የሽኝትና የጧፍ ማብራት ፕሮግራም ቤተሰቦቹ፣ ጓደኞቹ፣ የሙያ አጋሮቹና አድናቂዎቹ በተገኙበት ለረዥም ዓመታት በሙያው ባገለገለበት አንጋፋው ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት ግንቦት 25/ 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ በ3፡00 ሰዓት ላይ ከተከናወነ በኋላ የቀብር ሰነ ስርዓቱ በአማኑኤል ካቴድራል ቤተክርስቲያን ይፈፀማል።
የአዲስ አበባ ቴአትር ቤቶች አስተዳደር ድርጅት በመላው ሰራተኞቹና የሙያ አጋሮቹ ስም በሁለገቡ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ህልፈተ ህይወት የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን እየገለፀ ፈጣሪ ነፍሱን በመዓዛ ገነት እንዲያሳርፍ ይመኛል፡፡ እንዲሁም ለውድ ቤተሰቦቹ፣ ለዘመዶቹ፣ ለጓደኞቹ፣ ለስራ ባልደረቦቹ፣ ለሙያ አጋሮቹና አድናቂዎቹ በሙሉ ፈጣሪ ልባዊ መጽናናትን እንዲሰጣቸው ይመኛል፡፡
የአዲስ አበባ ቴአትር ቤቶች አስተዳደር ድርጅት-ኮምኒኬሽን
#ኪዳኔምስጋናው #ሀገርፍቅርቴአትር #የጥበብሰው #ሀዘን #ኪነጥበብ #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
4 days ago
ኪዱ አረፈ
#ethiopia | በተለያዩ የጥበብ ዘርፎች በስፋት የሚታወቀው አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ባደረበት ህመም በህክምና ሲረዳ ቆይቶ ግንቦት 23 ቀን 2018 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል።
የአርቲስቱ የቀብር ስነ ስርዓት ማክሰኞ ግንቦት 25 ቀን 2018 ዓ.ም በአማኑኤል ቤተክርስቲያን ከቀኑ 6:00 ሰዓት ይፈጸማል።
ከጠዋቱ 3:00 ሰዓት ጀምሮ በሙያ ህይወቱ በታማኝነት ባገለገለበት ታሪካዊው ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት የሽኝት እና የሻማ ማብራት መርሃ ግብር ይከናወናል።
***
የሁለገቡ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው አጭር የህይወት ታሪክ
የመድረኩ እንዝርት ሁለገቡ የጥበብ ሰው አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ከእናቱ ከወ/ሮ ብዙነሽ ጓንጉል እና ከአባቱ ከአቶ ምስጋናው ደርኬሮ ሰኔ 15/ 1958 ዓ.ም አዲስ አበባ ከተማ ልዩ ስሙ አማኑኤል አጂፕ ተብሎ በሚጠራዉ አካባቢ ተወለደ፡፡ ለአቅመ ፊደል ሲደርስ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርቱን በደጃዝማች ኃይሉ ተስፋዬ ትምህርት ቤት እንዲሁም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱን በአዲስ ከተማ ትምሀርት ቤት እስከ 12ኛ ክፍል ተምሮ አጠናቋል።
ከውዝዋዜ ጋር ገና ተማሪ እያለ የተወዳጀው ሁለገቡ ከያኒ ኪዳኔ ምስጋናው የጥበብ ጉዞውን በቀበሌ ኪነትና በከፍተኛ ኪነት ውስጥ አድርጎ መዳረሻውን በአዲስ አበባ ቴአትርና ባህል አዳራሽ በማድረግ በ1977 ዓ.ም በውዝዋዜ ሙያ ለመቀጠር በቅቷል፡፡ የአርቲስት ኪዳኔ የሙያ ፍቅር፣ ችሎታና ስነምግባር ያስደመማቸው የውዝዋዜ ክፍል አሰልጣኞችና ኃላፊዎች ከተወዛዋዥነት ወደ ረዳት አሰልጣኝነት እንዲያድግ በማድረጋቸው ከ1983-1990 ዓ.ም ድረስ በረዳት አሰልጣኝነት ሙያ ሲያገለግል ቆይቷል፡፡ ጥበበኛው ኪዳኒ በረዳትነት የጀመረውን የአሰልጣኝነት ስራውን ከፍ በማድረግ ከ1991 እሰከ 1992 በቋሚ አሰልጣኝነት ተመድቦ በርካታ ባለሙያዎችን በክህሎት፣ በስነምግባርና በጥበብ አሰልጥኖ ለውዝዋዜ ሙያ መስፋፋትና አድገት የበኩሉን ድርሻ አበርክቷል፡፡
በውዝዋዜ ጥበብ በማለዳው የተነደፈው ኪዳኔ በእውቀት፣ በልምድና በፈጠራ እየጎመራና አንቱታን እያተረፈ ሲመጣ አድማሱን በማስፋት በአንጋፋው ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት ተዛውሮ ከ1992 እሰከ 2007 ዓ.ም በዋና አሰልጣኝነትና በኬሮጋራፈርነት በርካታ በሀገር አቀፍና በአለም አቀፍ ደረጃ ግዘፍ የነሱ መድረኮች ላይ የቀረቡ የውዝዋዜ ስራዎችን በማዘጋጀት፣ በማማከርና በመምራት ከሰው ልብና አእምሮ የማይጠፉ ደማቅ ኪነጥበባዊ ስራዎችን ሰርቷል፡፡
አርቲስት ኪዳኔ ፈጣን የፈጠራ፣ የማደራጀትና የመምራት አቅም የነበረው ብርቱ የጥበብ ሰው ነበር፡፡ በርካታ ተወዛዋዦች የሚገኙበት የጥበብ መድረክ ካለ እዛ የጥበብ መድረክ ላይ ኪዳኔ መኖሩ ሳይታለም የተፈታ ህልም ነበር፡፡ የኪዳኔ የፈጠራ፣ የውዝዋዜ ችሎታና የውዝዋዜ ዝግጅት ጥበብ የታየባቸው አያሌ የውዝዋዜ ጥበብ ስራዎች ህያው መስክሮቹ ናቸው፡፡ በፋሽስት ጣሊያን የተዘረፈው የአክሱም ሀውልት ወደ ሀገሩ ሲመለስ ለነበረው አቀባበል በተዘጋጀው የኪነጥበብ መድረክ ላይ በአዲስ አበባና በአክሱም ከተማ ግዙፍ የውዝዋዜ ዝግጅት፣ በህዳሴ ግድብ ማስተባበሪያ በተዘጋጀው የጥበብ መድረክ፣ በሚሊኒዬም አዳራሽ፣ በባህዳር ጣና ሐይቅ ላይ የውዝዋዜ የጀልባ ላይ ትርኢት፣ የአዲስ ዓመት የበዓል ዝግጅቶች ላይ ጥበብ፣ ባህል፣ ፈጠራና ውበት የተመላባቸው በርካታ ተወዛዋዦች የተሳተፉባቸውን የጥበብ ስራዎች በማዘጋጀት የጥበብና የሀገር ባለውለታነቱን አስመስክሯል፡፡
በአንጋፋው ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት ከአስራ አምስት ዓመት በላይ በአሰልጣኝነት ሲሰራ ከቆየ በኋላ ከ2007 እስከ 2017 ዓ.ም ድረስ ወደ ቀድሞ የሙያ ቤቱ የአዲስ አበባ ቴአትርና ባህል አደራሽ ተዛውሮ በአሰልጣኝነትና በኬሮግራፈርነት ሲሰራ ቆይቷል፡፡
አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ከተወዛዋዠነት፣ አሰልጣኝነት፣ አዘጋጅነትና አማካሪነት ባሻገር በድምጻዊነትና በቴአትርና ፊልም ተዋናይነትም በመሳተፍ ሁለገብ ከያኒነቱን ያስመሰከረ ድንቅ ጥበበኛ ነበር፡፡ በርካታ የሙዚቃ ቪዲዮ ስራዎች ላይ የኪዳኔ ደማቅ የፈጠራና የጥበብ አሻራ ያረፈባቸው ውዝዋዜዎችና ዝግጅቶች ዛሬም፣ ነገም ህያው ምስክሮች ናቸው፡፡
አሰልጣኝና ኬሮግራፍር እንዲሁም የውዝዋዜ አማካሪ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው በሞያው በሰራባቸው አመታት በርካታ
1. ባለሙያዎች ወደ ሙያው እንዲገቡና የሙያው ስነምግባር እንዲኖራቸው አደርጓል፡፡
2. የባህል ውዝዋዜ ትምህርት ቤት በሌለበት ዘመን በቴአትር ቤቶችና ከቴአትር ቤቶች ውጪ የነበሩ ወጣቶችን አሰልጥናል፤
3. ከከተማ ውጪ በመሄድ ቱባ ባህሎችን በማጥናትና በማምጣት የተለያዩ የባህል ጭፈራዎችንና አለባበሶችን አስተዋውቋል፡፡
4. የውዝዋዜ ሙያ እንደሙያ እንዲታይና አሁን የደረሰበት ደረጃ ላይ እንዲደርስ የተለያዩ መድረኮች ላይ እና ጥናቶች ላይ በመሳተፍ አስተዋኦ አበርክቷል፡፡
5. በአዲስ አበባ ከተማ በተዘጋጁ በርካታ የኪነ ጥበብ ፌስቲቫሎች ላይ በመጋበዝ በዳኝነትና በአማካሪነት ሰርቷል፡፡
6. ከአዲስ አበባ ውጪ በተለያዩ ክልሎች የሚገኙ ወጣቶችን ከማሰልጠን አልፎ በደቡብ ክልል ውስጥ የባህል ባንድ ለማቋቋም በቅቷል፡፡
7. በከተማችንና በተለያዩ ከተሞች በተከበሩ የብሄሔር ብሄረሰቦች ክብረ በዓላት ላይ የጥበብ ስራዎችን አቅርባል፡፡
8. በተለያዩ ጊዜ የተከበሩ የአደባበይ በአላት አድዋና የካቲት12 የመሳሰሉት ላይ ስራዋችን አቅርባል፡፡
9. በታላቁ ህዳሴ ግድብ ድረስ በመሄድና ታስቦ በሚከበርበት ጊዜም ስራዎችን አቅርቧል፡፡
10. በመንግስት መስረታና በበአለ ሲመቱ ዝግጅት ላይ ታላቅ የውዝዋዜ ትርኢት በኬሮግራፈርነት ሰርቷል፡፡
11. ሀገራችን የጦርነትና የተፈጥሮ ችግር በገጠማት ጊዜ ከኪነ ጥበብ ስራው ጋር ቀዳሚ በመሆን በርካታ አነቃቂ ስራዎችን ሰርቷል፡፡
12. የተለያዩ የሀገር መሪዎች፣ አንባሳደሮችና ዲፕሎማቶች ሲመጡና ሲሸኙ በአየር መንገድና በከንቲባ ጽ/ቤት ግቢ ውስጥ ደማቅ አቀባበል በማደረግ እና ትርኢቶችን በማቅረብ ባህላችንን አስተዋውቋል፡፡
13. በከተማ ደረጃ የሚዘጋጁ ትላልቅ ሴሚናሮች፤ጉባኤዋችና ሲንፖዚየሞች ላይ የተለያዩ የኬሮግራፈር ስራዎችን ሰርቷል፡፡
ሁለገቡ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ላበረከታቸው ኪነጥበባዊ ስራዎች የምስጋናና የእውቅና የምስክር ወረቀቶችን፡-
Ø ከኢፌድሪ ፊዴሬሽን ምክር ቤት
Ø ከኢፌድሪ ባህልና ቱሪዝም ሚንስቴር
Ø አዲስ አበባ ዩንቪርስቲ
Ø ከአዲስ አበባ ባህል ኪነ የጥበብና ቱሪዝም ቢሮ
Ø ከታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ማስተባበሪያ ጽ/ቤት
Ø ከሀገር ፍቅር፤ከቴአትርና ባህል አደራሽ፤ከራስ ቴአትር፤ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአተር እና ሌሎችም በርካታ ተቋማት በክብር ተቀብሏል፡፡
አሰልጣኝ፣ ኬሮግራፍርና የውዝዋዜ አማካሪ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ሙያው እንዲያድግና ባለሙያውም እንዲጠቀም በነበረው ፍላጎትና ቁጭት ምክንያት ሙያው በተለያዩ ትልልቅ ሆቴሎችና የባህል ምሽቶች እንዲሰራና ባህላችን የበለጠ እንዲተዋወቅ በማማከርና በመደገፍ የአንበሳውን ድርሻ ይወስዳል፡፡
አርቲስት ኪዳኔ ከበርካታ የሀገራችን ታዋቂና ተወዳጅ ሙዚቀኞች ጋር ትላልቅ መድረኮችና በከተማ ደረጃ በቀረቡ ታላላቅ ህዝባዊ በአላትና የሙዚቃ ኮንሰርቶች ላይ የኪሮግራፈር ስራዋችን
Ø በሸራተን አዲስ ሆቴል
Ø በሚሊንየም አዳራሽ
Ø በኢግዚብሽን ማዕከል
Ø በመስቀል አደባባይ
Ø በአዲስ አበባ ስቴድየም
Ø በጊዮን ሆቴል
Ø በሂልተን ሆቴል
Ø በስካይላት ሆቴል በመገኘት ጥበባዊ ስራዎችን ያቀረበ ሲሆን ትልልቅ የቀጥታ የቴሌብዥን ስርጭ የነበራቸውን ግዙፍ መድረኮችም ላይ ልዩ የኬሮግራፈርነት ሙያውን ድንቅ ብቃት አስመስክሯል፡፡
አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው በተለያዩ ቴአትርና ሙዚቃዊ ቴአትሮች ላይ በትወናና በዝግጅት ሰርቷል፡፡ በትወና የተሳተፈባቸው ስራዎች፦
Ø ጤና ያጣ ፍቅር
Ø ሮሚዮና ጁሌት
Ø የቀለጠው መንድር
Ø ሊስትሮ ኦፔራ
Ø ከልሺን አውልቂ
Ø ፎርፌ
Ø ኦቴሎ
Ø ቴዎድሮስ
በሙዚቃዊ ድራማ ኬሮግራፈር ዝግጅት፡-
Ø ፎርፌ
Ø ኢትዮጵያዊነት ጥልቅ ነው
Ø ከልሽን አውልቂ
Ø ሊስትሮ ኦፔራ
Ø ሉሲ
Ø ሀገር ማለት ሰው ነው እና ሌሎችም የጠቀሳሉ፡፡
በፊልም ትወና፡-
Ø በህይወት ዙሪያ
Ø ሔሮሽማ
አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ከመድረክ ስራዎቹ በተጨማሪም በተላያዩ ታዋቂና አንጋፍ እንዲሁም ወጣት ድምጻውያን የሙዚቃ ቪዲዮ ስራዎች ላይ በኬሮግራፈርነትና በአማካሪነት ሰርቷል፡፡
Ø ለክብር ዳ/ር ጥላሁን ገሠሠ
Ø ለድምፃዊ ኤፍሬም ታምሩ የሰራቸው ስራዎች ጥቂቶቹ ናቸው፡፡
አርቲስት ኪዳኔ በተለያዩ የቴሌቪዥን ዝግጅቶችና የበዓል ፕሮግራሞች ላይ ባቀረባቸው የጥበብ ስራዎች ውበትና ድምቀት የነበረ ሲሆን በፋና ቴሌቭዥን ፋና ሰማንያ የውዝዋዜና ዳንስ ተሰጥኦ ውድድር ላይ በአማካሪነት በመስራት ሙያዊ አስተዋፅዎ አድርጓል፡፡
ሁለገቡ አርቲስት ኪዳኔ በሙያው አድማስ ተሸግሮ በዱባይ እና በታይላንድ ኢትዮጰያንና ባህሏን ያስተዋወቀ ብርቱ የጥበብ ሰው ሰሆን በቅርብ በሀገራችን እና በአለም ህዝቦች ዘንድ አንድ ጊዜ ተሰርቶ ያልተደገመውን የህዝብ ለህዝብ ተጓዥ የሙዚቃ የባህል ቡድንን የሚያስታውስ የሀገረሰብ ሙዚቃዎችን፣ ጭፈራዎችንና ባህላችንን የሚያስተዋውቅ ሉሲ ድንቅነሽ ኢትዮጵያ በሚል በመላው ሀገር ተዟዙሮ የቀረበውን ትርኢት ከባህል ሚንስቴር ኃላፊነት ተሰጥቶት በዋና አዘጋጅነት የውዝዋዜውን ዝግጅት መምራት የቻለ ድንቅ ጥበበኛ ነበር፡፡
ሁለገቡ ከያኒ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ከ2017 ዓ.ም ጀምሮ ህይወቱ እስካለፈበት ግንቦት 23/2018 ዓ.ም ድረስ በአንጋፋው ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት ተዛውሮ በሙያው ወገኑን፣ ሀገሩንና ሙያውን በጥበብ፣ በታማኝነትና በትጋት ሲያገለግል የኖረ፣ በጥበብ ስራዎቹ ስሙን ከመቃብር በላይ ማኖር የቻለ ታላቅ ጥበበኛ ነበር፡፡
አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናዉ የጋብቻ ህይወቱን ከረዥም ጊዜ ፍቅረኛዉ ከወ/ት አይናለም ተፈራ ጋር የካቲት 2 /2018 በክብር ፈፅሟል። ይሁንና ይህ ታላቅ ጥበበኛ ባጋጠመው የጤና እክል ሳቢያ በአዲስ ህይወት አጠቃላይ ሆስፒታል እና በሆፕ ሆስፒታል በህክምና ሲረዳ ቆይቶ ግንቦት 23/2018 ዓ.ም በተወለደ በ60 ዓመቱ ከዚህ ዓለም ድካም አርፏል፡፡
የአርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው የሽኝትና የጧፍ ማብራት ፕሮግራም ቤተሰቦቹ፣ ጓደኞቹ፣ የሙያ አጋሮቹና አድናቂዎቹ በተገኙበት ለረዥም ዓመታት በሙያው ባገለገለበት አንጋፋው ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት ግንቦት 25/ 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ በ3፡00 ሰዓት ላይ ከተከናወነ በኋላ የቀብር ሰነ ስርዓቱ በአማኑኤል ካቴድራል ቤተክርስቲያን ይፈፀማል።
የአዲስ አበባ ቴአትር ቤቶች አስተዳደር ድርጅት በመላው ሰራተኞቹና የሙያ አጋሮቹ ስም በሁለገቡ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ህልፈተ ህይወት የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን እየገለፀ ፈጣሪ ነፍሱን በመዓዛ ገነት እንዲያሳርፍ ይመኛል፡፡ እንዲሁም ለውድ ቤተሰቦቹ፣ ለዘመዶቹ፣ ለጓደኞቹ፣ ለስራ ባልደረቦቹ፣ ለሙያ አጋሮቹና አድናቂዎቹ በሙሉ ፈጣሪ ልባዊ መጽናናትን እንዲሰጣቸው ይመኛል፡፡
የአዲስ አበባ ቴአትር ቤቶች አስተዳደር ድርጅት-ኮምኒኬሽን
#ኪዳኔምስጋናው #ሀገርፍቅርቴአትር #የጥበብሰው #ሀዘን #ኪነጥበብ #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | በተለያዩ የጥበብ ዘርፎች በስፋት የሚታወቀው አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ባደረበት ህመም በህክምና ሲረዳ ቆይቶ ግንቦት 23 ቀን 2018 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል።
የአርቲስቱ የቀብር ስነ ስርዓት ማክሰኞ ግንቦት 25 ቀን 2018 ዓ.ም በአማኑኤል ቤተክርስቲያን ከቀኑ 6:00 ሰዓት ይፈጸማል።
ከጠዋቱ 3:00 ሰዓት ጀምሮ በሙያ ህይወቱ በታማኝነት ባገለገለበት ታሪካዊው ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት የሽኝት እና የሻማ ማብራት መርሃ ግብር ይከናወናል።
***
የሁለገቡ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው አጭር የህይወት ታሪክ
የመድረኩ እንዝርት ሁለገቡ የጥበብ ሰው አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ከእናቱ ከወ/ሮ ብዙነሽ ጓንጉል እና ከአባቱ ከአቶ ምስጋናው ደርኬሮ ሰኔ 15/ 1958 ዓ.ም አዲስ አበባ ከተማ ልዩ ስሙ አማኑኤል አጂፕ ተብሎ በሚጠራዉ አካባቢ ተወለደ፡፡ ለአቅመ ፊደል ሲደርስ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርቱን በደጃዝማች ኃይሉ ተስፋዬ ትምህርት ቤት እንዲሁም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱን በአዲስ ከተማ ትምሀርት ቤት እስከ 12ኛ ክፍል ተምሮ አጠናቋል።
ከውዝዋዜ ጋር ገና ተማሪ እያለ የተወዳጀው ሁለገቡ ከያኒ ኪዳኔ ምስጋናው የጥበብ ጉዞውን በቀበሌ ኪነትና በከፍተኛ ኪነት ውስጥ አድርጎ መዳረሻውን በአዲስ አበባ ቴአትርና ባህል አዳራሽ በማድረግ በ1977 ዓ.ም በውዝዋዜ ሙያ ለመቀጠር በቅቷል፡፡ የአርቲስት ኪዳኔ የሙያ ፍቅር፣ ችሎታና ስነምግባር ያስደመማቸው የውዝዋዜ ክፍል አሰልጣኞችና ኃላፊዎች ከተወዛዋዥነት ወደ ረዳት አሰልጣኝነት እንዲያድግ በማድረጋቸው ከ1983-1990 ዓ.ም ድረስ በረዳት አሰልጣኝነት ሙያ ሲያገለግል ቆይቷል፡፡ ጥበበኛው ኪዳኒ በረዳትነት የጀመረውን የአሰልጣኝነት ስራውን ከፍ በማድረግ ከ1991 እሰከ 1992 በቋሚ አሰልጣኝነት ተመድቦ በርካታ ባለሙያዎችን በክህሎት፣ በስነምግባርና በጥበብ አሰልጥኖ ለውዝዋዜ ሙያ መስፋፋትና አድገት የበኩሉን ድርሻ አበርክቷል፡፡
በውዝዋዜ ጥበብ በማለዳው የተነደፈው ኪዳኔ በእውቀት፣ በልምድና በፈጠራ እየጎመራና አንቱታን እያተረፈ ሲመጣ አድማሱን በማስፋት በአንጋፋው ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት ተዛውሮ ከ1992 እሰከ 2007 ዓ.ም በዋና አሰልጣኝነትና በኬሮጋራፈርነት በርካታ በሀገር አቀፍና በአለም አቀፍ ደረጃ ግዘፍ የነሱ መድረኮች ላይ የቀረቡ የውዝዋዜ ስራዎችን በማዘጋጀት፣ በማማከርና በመምራት ከሰው ልብና አእምሮ የማይጠፉ ደማቅ ኪነጥበባዊ ስራዎችን ሰርቷል፡፡
አርቲስት ኪዳኔ ፈጣን የፈጠራ፣ የማደራጀትና የመምራት አቅም የነበረው ብርቱ የጥበብ ሰው ነበር፡፡ በርካታ ተወዛዋዦች የሚገኙበት የጥበብ መድረክ ካለ እዛ የጥበብ መድረክ ላይ ኪዳኔ መኖሩ ሳይታለም የተፈታ ህልም ነበር፡፡ የኪዳኔ የፈጠራ፣ የውዝዋዜ ችሎታና የውዝዋዜ ዝግጅት ጥበብ የታየባቸው አያሌ የውዝዋዜ ጥበብ ስራዎች ህያው መስክሮቹ ናቸው፡፡ በፋሽስት ጣሊያን የተዘረፈው የአክሱም ሀውልት ወደ ሀገሩ ሲመለስ ለነበረው አቀባበል በተዘጋጀው የኪነጥበብ መድረክ ላይ በአዲስ አበባና በአክሱም ከተማ ግዙፍ የውዝዋዜ ዝግጅት፣ በህዳሴ ግድብ ማስተባበሪያ በተዘጋጀው የጥበብ መድረክ፣ በሚሊኒዬም አዳራሽ፣ በባህዳር ጣና ሐይቅ ላይ የውዝዋዜ የጀልባ ላይ ትርኢት፣ የአዲስ ዓመት የበዓል ዝግጅቶች ላይ ጥበብ፣ ባህል፣ ፈጠራና ውበት የተመላባቸው በርካታ ተወዛዋዦች የተሳተፉባቸውን የጥበብ ስራዎች በማዘጋጀት የጥበብና የሀገር ባለውለታነቱን አስመስክሯል፡፡
በአንጋፋው ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት ከአስራ አምስት ዓመት በላይ በአሰልጣኝነት ሲሰራ ከቆየ በኋላ ከ2007 እስከ 2017 ዓ.ም ድረስ ወደ ቀድሞ የሙያ ቤቱ የአዲስ አበባ ቴአትርና ባህል አደራሽ ተዛውሮ በአሰልጣኝነትና በኬሮግራፈርነት ሲሰራ ቆይቷል፡፡
አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ከተወዛዋዠነት፣ አሰልጣኝነት፣ አዘጋጅነትና አማካሪነት ባሻገር በድምጻዊነትና በቴአትርና ፊልም ተዋናይነትም በመሳተፍ ሁለገብ ከያኒነቱን ያስመሰከረ ድንቅ ጥበበኛ ነበር፡፡ በርካታ የሙዚቃ ቪዲዮ ስራዎች ላይ የኪዳኔ ደማቅ የፈጠራና የጥበብ አሻራ ያረፈባቸው ውዝዋዜዎችና ዝግጅቶች ዛሬም፣ ነገም ህያው ምስክሮች ናቸው፡፡
አሰልጣኝና ኬሮግራፍር እንዲሁም የውዝዋዜ አማካሪ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው በሞያው በሰራባቸው አመታት በርካታ
1. ባለሙያዎች ወደ ሙያው እንዲገቡና የሙያው ስነምግባር እንዲኖራቸው አደርጓል፡፡
2. የባህል ውዝዋዜ ትምህርት ቤት በሌለበት ዘመን በቴአትር ቤቶችና ከቴአትር ቤቶች ውጪ የነበሩ ወጣቶችን አሰልጥናል፤
3. ከከተማ ውጪ በመሄድ ቱባ ባህሎችን በማጥናትና በማምጣት የተለያዩ የባህል ጭፈራዎችንና አለባበሶችን አስተዋውቋል፡፡
4. የውዝዋዜ ሙያ እንደሙያ እንዲታይና አሁን የደረሰበት ደረጃ ላይ እንዲደርስ የተለያዩ መድረኮች ላይ እና ጥናቶች ላይ በመሳተፍ አስተዋኦ አበርክቷል፡፡
5. በአዲስ አበባ ከተማ በተዘጋጁ በርካታ የኪነ ጥበብ ፌስቲቫሎች ላይ በመጋበዝ በዳኝነትና በአማካሪነት ሰርቷል፡፡
6. ከአዲስ አበባ ውጪ በተለያዩ ክልሎች የሚገኙ ወጣቶችን ከማሰልጠን አልፎ በደቡብ ክልል ውስጥ የባህል ባንድ ለማቋቋም በቅቷል፡፡
7. በከተማችንና በተለያዩ ከተሞች በተከበሩ የብሄሔር ብሄረሰቦች ክብረ በዓላት ላይ የጥበብ ስራዎችን አቅርባል፡፡
8. በተለያዩ ጊዜ የተከበሩ የአደባበይ በአላት አድዋና የካቲት12 የመሳሰሉት ላይ ስራዋችን አቅርባል፡፡
9. በታላቁ ህዳሴ ግድብ ድረስ በመሄድና ታስቦ በሚከበርበት ጊዜም ስራዎችን አቅርቧል፡፡
10. በመንግስት መስረታና በበአለ ሲመቱ ዝግጅት ላይ ታላቅ የውዝዋዜ ትርኢት በኬሮግራፈርነት ሰርቷል፡፡
11. ሀገራችን የጦርነትና የተፈጥሮ ችግር በገጠማት ጊዜ ከኪነ ጥበብ ስራው ጋር ቀዳሚ በመሆን በርካታ አነቃቂ ስራዎችን ሰርቷል፡፡
12. የተለያዩ የሀገር መሪዎች፣ አንባሳደሮችና ዲፕሎማቶች ሲመጡና ሲሸኙ በአየር መንገድና በከንቲባ ጽ/ቤት ግቢ ውስጥ ደማቅ አቀባበል በማደረግ እና ትርኢቶችን በማቅረብ ባህላችንን አስተዋውቋል፡፡
13. በከተማ ደረጃ የሚዘጋጁ ትላልቅ ሴሚናሮች፤ጉባኤዋችና ሲንፖዚየሞች ላይ የተለያዩ የኬሮግራፈር ስራዎችን ሰርቷል፡፡
ሁለገቡ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ላበረከታቸው ኪነጥበባዊ ስራዎች የምስጋናና የእውቅና የምስክር ወረቀቶችን፡-
Ø ከኢፌድሪ ፊዴሬሽን ምክር ቤት
Ø ከኢፌድሪ ባህልና ቱሪዝም ሚንስቴር
Ø አዲስ አበባ ዩንቪርስቲ
Ø ከአዲስ አበባ ባህል ኪነ የጥበብና ቱሪዝም ቢሮ
Ø ከታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ማስተባበሪያ ጽ/ቤት
Ø ከሀገር ፍቅር፤ከቴአትርና ባህል አደራሽ፤ከራስ ቴአትር፤ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአተር እና ሌሎችም በርካታ ተቋማት በክብር ተቀብሏል፡፡
አሰልጣኝ፣ ኬሮግራፍርና የውዝዋዜ አማካሪ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ሙያው እንዲያድግና ባለሙያውም እንዲጠቀም በነበረው ፍላጎትና ቁጭት ምክንያት ሙያው በተለያዩ ትልልቅ ሆቴሎችና የባህል ምሽቶች እንዲሰራና ባህላችን የበለጠ እንዲተዋወቅ በማማከርና በመደገፍ የአንበሳውን ድርሻ ይወስዳል፡፡
አርቲስት ኪዳኔ ከበርካታ የሀገራችን ታዋቂና ተወዳጅ ሙዚቀኞች ጋር ትላልቅ መድረኮችና በከተማ ደረጃ በቀረቡ ታላላቅ ህዝባዊ በአላትና የሙዚቃ ኮንሰርቶች ላይ የኪሮግራፈር ስራዋችን
Ø በሸራተን አዲስ ሆቴል
Ø በሚሊንየም አዳራሽ
Ø በኢግዚብሽን ማዕከል
Ø በመስቀል አደባባይ
Ø በአዲስ አበባ ስቴድየም
Ø በጊዮን ሆቴል
Ø በሂልተን ሆቴል
Ø በስካይላት ሆቴል በመገኘት ጥበባዊ ስራዎችን ያቀረበ ሲሆን ትልልቅ የቀጥታ የቴሌብዥን ስርጭ የነበራቸውን ግዙፍ መድረኮችም ላይ ልዩ የኬሮግራፈርነት ሙያውን ድንቅ ብቃት አስመስክሯል፡፡
አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው በተለያዩ ቴአትርና ሙዚቃዊ ቴአትሮች ላይ በትወናና በዝግጅት ሰርቷል፡፡ በትወና የተሳተፈባቸው ስራዎች፦
Ø ጤና ያጣ ፍቅር
Ø ሮሚዮና ጁሌት
Ø የቀለጠው መንድር
Ø ሊስትሮ ኦፔራ
Ø ከልሺን አውልቂ
Ø ፎርፌ
Ø ኦቴሎ
Ø ቴዎድሮስ
በሙዚቃዊ ድራማ ኬሮግራፈር ዝግጅት፡-
Ø ፎርፌ
Ø ኢትዮጵያዊነት ጥልቅ ነው
Ø ከልሽን አውልቂ
Ø ሊስትሮ ኦፔራ
Ø ሉሲ
Ø ሀገር ማለት ሰው ነው እና ሌሎችም የጠቀሳሉ፡፡
በፊልም ትወና፡-
Ø በህይወት ዙሪያ
Ø ሔሮሽማ
አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ከመድረክ ስራዎቹ በተጨማሪም በተላያዩ ታዋቂና አንጋፍ እንዲሁም ወጣት ድምጻውያን የሙዚቃ ቪዲዮ ስራዎች ላይ በኬሮግራፈርነትና በአማካሪነት ሰርቷል፡፡
Ø ለክብር ዳ/ር ጥላሁን ገሠሠ
Ø ለድምፃዊ ኤፍሬም ታምሩ የሰራቸው ስራዎች ጥቂቶቹ ናቸው፡፡
አርቲስት ኪዳኔ በተለያዩ የቴሌቪዥን ዝግጅቶችና የበዓል ፕሮግራሞች ላይ ባቀረባቸው የጥበብ ስራዎች ውበትና ድምቀት የነበረ ሲሆን በፋና ቴሌቭዥን ፋና ሰማንያ የውዝዋዜና ዳንስ ተሰጥኦ ውድድር ላይ በአማካሪነት በመስራት ሙያዊ አስተዋፅዎ አድርጓል፡፡
ሁለገቡ አርቲስት ኪዳኔ በሙያው አድማስ ተሸግሮ በዱባይ እና በታይላንድ ኢትዮጰያንና ባህሏን ያስተዋወቀ ብርቱ የጥበብ ሰው ሰሆን በቅርብ በሀገራችን እና በአለም ህዝቦች ዘንድ አንድ ጊዜ ተሰርቶ ያልተደገመውን የህዝብ ለህዝብ ተጓዥ የሙዚቃ የባህል ቡድንን የሚያስታውስ የሀገረሰብ ሙዚቃዎችን፣ ጭፈራዎችንና ባህላችንን የሚያስተዋውቅ ሉሲ ድንቅነሽ ኢትዮጵያ በሚል በመላው ሀገር ተዟዙሮ የቀረበውን ትርኢት ከባህል ሚንስቴር ኃላፊነት ተሰጥቶት በዋና አዘጋጅነት የውዝዋዜውን ዝግጅት መምራት የቻለ ድንቅ ጥበበኛ ነበር፡፡
ሁለገቡ ከያኒ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ከ2017 ዓ.ም ጀምሮ ህይወቱ እስካለፈበት ግንቦት 23/2018 ዓ.ም ድረስ በአንጋፋው ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት ተዛውሮ በሙያው ወገኑን፣ ሀገሩንና ሙያውን በጥበብ፣ በታማኝነትና በትጋት ሲያገለግል የኖረ፣ በጥበብ ስራዎቹ ስሙን ከመቃብር በላይ ማኖር የቻለ ታላቅ ጥበበኛ ነበር፡፡
አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናዉ የጋብቻ ህይወቱን ከረዥም ጊዜ ፍቅረኛዉ ከወ/ት አይናለም ተፈራ ጋር የካቲት 2 /2018 በክብር ፈፅሟል። ይሁንና ይህ ታላቅ ጥበበኛ ባጋጠመው የጤና እክል ሳቢያ በአዲስ ህይወት አጠቃላይ ሆስፒታል እና በሆፕ ሆስፒታል በህክምና ሲረዳ ቆይቶ ግንቦት 23/2018 ዓ.ም በተወለደ በ60 ዓመቱ ከዚህ ዓለም ድካም አርፏል፡፡
የአርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው የሽኝትና የጧፍ ማብራት ፕሮግራም ቤተሰቦቹ፣ ጓደኞቹ፣ የሙያ አጋሮቹና አድናቂዎቹ በተገኙበት ለረዥም ዓመታት በሙያው ባገለገለበት አንጋፋው ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት ግንቦት 25/ 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ በ3፡00 ሰዓት ላይ ከተከናወነ በኋላ የቀብር ሰነ ስርዓቱ በአማኑኤል ካቴድራል ቤተክርስቲያን ይፈፀማል።
የአዲስ አበባ ቴአትር ቤቶች አስተዳደር ድርጅት በመላው ሰራተኞቹና የሙያ አጋሮቹ ስም በሁለገቡ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ህልፈተ ህይወት የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን እየገለፀ ፈጣሪ ነፍሱን በመዓዛ ገነት እንዲያሳርፍ ይመኛል፡፡ እንዲሁም ለውድ ቤተሰቦቹ፣ ለዘመዶቹ፣ ለጓደኞቹ፣ ለስራ ባልደረቦቹ፣ ለሙያ አጋሮቹና አድናቂዎቹ በሙሉ ፈጣሪ ልባዊ መጽናናትን እንዲሰጣቸው ይመኛል፡፡
የአዲስ አበባ ቴአትር ቤቶች አስተዳደር ድርጅት-ኮምኒኬሽን
#ኪዳኔምስጋናው #ሀገርፍቅርቴአትር #የጥበብሰው #ሀዘን #ኪነጥበብ #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
11 days ago
የዘማሪ ቃልኪዳን ጥላሁን (ሊሊ) እናት ወይዘሮ ቅድስት ጳውሎስ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ
#ethiopia | በአዲስ አበባ ማዘጋጃ ቤት ውስጥ በበጀትና ሂሳብ ባለሙያነት ለረጅም ጊዜ ሲያገለግሉ የቆዩት ወይዘሮ ቅድስት ጳውሎስ ተድላ በ74 ዓመታቸው አርፈዋል።
የሽኝት እና የቀብር ሥነ ሥርዓታቸውም በግንቦት 19 ቀን 2018 ዓ.ም በአሜሪካ ሜሪላንድ ግዛት ውስጥ እንደሚፈጸም ታውቋል።
ባለፈው ወር በዩናይትድ ስቴትስ 74ኛ ዓመት የልደት በዓላቸውን ያከበሩት ወይዘሮ ቅድስት አምስት ልጆቻቸውን በጥሩ ሥነ ምግባርና በትጋት ያሳደጉ ጠንካራ እናት ነበሩ።
የታዋቂዋ ዘማሪ ቃልኪዳን ጥላሁን (ሊሊ) እንዲሁም የዶክተር ለዓለም ጥላሁን፣ የጂጂ ጥላሁን፣ የኪኪ ጥላሁን እና የዳግማዊ ጥላሁን እናት የሆኑት ወይዘሮ ቅድስት ጳውሎስ ላለፉት 13 ዓመታት መኖሪያቸውን በአሜሪካ አድርገው ቆይተዋል።
ልጆቻቸውና የልጅ ልጆቻቸው በሙሉ በውጭ ሀገር የሚኖሩ በመሆኑ የቀብር ሥነ ሥርዓቱ እሮብ ዕለት በሜሪላንድ እንደሚፈጸም ከቅርብ ቤተሰቦቻቸው የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
የሟች ሙሉ የሕይወት ታሪክ በቅርቡ በተወዳጅ ሚዲያ ዲጂታል አማራጮች የሚቀርብ ሲሆን ለተባረከው ቤተሰብ በሙሉ መጽናናትን እንመኛለን።
#ሊሊ_ጥላሁን #ቃልኪዳን_ጥላሁን #የቀብር_ሥነ_ሥርዓት #ሀዘን #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | በአዲስ አበባ ማዘጋጃ ቤት ውስጥ በበጀትና ሂሳብ ባለሙያነት ለረጅም ጊዜ ሲያገለግሉ የቆዩት ወይዘሮ ቅድስት ጳውሎስ ተድላ በ74 ዓመታቸው አርፈዋል።
የሽኝት እና የቀብር ሥነ ሥርዓታቸውም በግንቦት 19 ቀን 2018 ዓ.ም በአሜሪካ ሜሪላንድ ግዛት ውስጥ እንደሚፈጸም ታውቋል።
ባለፈው ወር በዩናይትድ ስቴትስ 74ኛ ዓመት የልደት በዓላቸውን ያከበሩት ወይዘሮ ቅድስት አምስት ልጆቻቸውን በጥሩ ሥነ ምግባርና በትጋት ያሳደጉ ጠንካራ እናት ነበሩ።
የታዋቂዋ ዘማሪ ቃልኪዳን ጥላሁን (ሊሊ) እንዲሁም የዶክተር ለዓለም ጥላሁን፣ የጂጂ ጥላሁን፣ የኪኪ ጥላሁን እና የዳግማዊ ጥላሁን እናት የሆኑት ወይዘሮ ቅድስት ጳውሎስ ላለፉት 13 ዓመታት መኖሪያቸውን በአሜሪካ አድርገው ቆይተዋል።
ልጆቻቸውና የልጅ ልጆቻቸው በሙሉ በውጭ ሀገር የሚኖሩ በመሆኑ የቀብር ሥነ ሥርዓቱ እሮብ ዕለት በሜሪላንድ እንደሚፈጸም ከቅርብ ቤተሰቦቻቸው የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
የሟች ሙሉ የሕይወት ታሪክ በቅርቡ በተወዳጅ ሚዲያ ዲጂታል አማራጮች የሚቀርብ ሲሆን ለተባረከው ቤተሰብ በሙሉ መጽናናትን እንመኛለን።
#ሊሊ_ጥላሁን #ቃልኪዳን_ጥላሁን #የቀብር_ሥነ_ሥርዓት #ሀዘን #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
11 days ago
"በጎዳና ላይ ካገኛችሁኝ መጥታችሁ እቀፉኝ" - ፔፕ ጋርድዮላ
* ጠዋት ተነስቶ ስፖርት መሥራት ቀረ !
#ethiopia | ለማንቸስተር ሲቲ ስኬታማ የአስር አመታት ጉዞ የጀርባ አጥንት የነበረው ስፓኝያዊው አሰልጣኝ ፔፕ ጋርድዮላ፣ ቡድኑ በኢትሃድ ስታዲየም ከአስቶንቪላ ጋር ካደረገው የውድድር አመቱ የመጨረሻ ጨዋታ በኋላ ደማቅ የሽኝት መርሃ ግብር ተዘካሂዷል።
ጋርድዮላ በስሜት ተውጦ እና እንባ እየተናነቀው "ይህን ያህል ፍቅር ለምን ሰጣችሁኝ?" በማለት ንግግሩን በጀመረበት ወቅት፣ በስታዲየሙ የታደሙት ደጋፊዎች በከፍተኛ ድምፅ ስሙን በመጥራትና የምስጋና መዝሙራትን በመዘመር ንግግሩን በተደጋጋሚ ያቋርጡት ነበር።
በስንብት ፕሮግራሙ ማጠቃለያ ላይም አሰልጣኙ ለክለቡ ደጋፊዎች ባስተላለፈው መልእክት "ወደየቤታችሁ ከመሄዳችሁ በፊት አንድ ነገር እንድናገር ፍቀዱልኝ፤ በቀጣዮቹ አመታት እዚህ ማንቸስተር ውስጥም ሆነ በማንኛውም የአውሮፓ ከተማ መንገድ ላይ ስታገኙኝ መጥታችሁ ሳታቅፉኝ እንዳታልፉ" ሲል የተማጸነ ሲሆን፣ ይህ ልብ የሚነካ መልእክቱ በአለም ዙሪያ በሚገኙ የክለቡ ደጋፊዎች ዘንድ በሰፊው እየተጋራ ይገኛል።
ፔፕ ጋርድዮላ በማንቸስተር ሲቲ ቆይታው ቡድኑን በ593 ጨዋታዎች ላይ መምራት የቻለ ሲሆን፣ የቀድሞውን አሰልጣኝ የሌዊስ ማክዶውልን የ592 ጨዋታዎች ክብረ ወሰን በመስበር በክለቡ ታሪክ ረጅም ጨዋታዎችን በመምራት ቀዳሚው መሆን ችሏል።
በእነዚህ ጨዋታዎች ውስጥም 416 ድሎችን ሲያስመዘግብ፣ 86 ጊዜ አቻ ወጥቶ በ91ዱ ደግሞ ሽንፈትን አስተናግዷል። በአጠቃላይ በአሰልጣኝነት ዘመኑ 20 ዋና ዋና ዋንጫዎችን ለክለቡ ያስገኘ ሲሆን፣ 5 ጊዜም የኢንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ የአመቱ ምርጥ አሰልጣኝ በመሆን መመረጡ ይታወሳል።
via ዮናታን አየለ
#manchestercity #pepguardiola #football #pep #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
* ጠዋት ተነስቶ ስፖርት መሥራት ቀረ !
#ethiopia | ለማንቸስተር ሲቲ ስኬታማ የአስር አመታት ጉዞ የጀርባ አጥንት የነበረው ስፓኝያዊው አሰልጣኝ ፔፕ ጋርድዮላ፣ ቡድኑ በኢትሃድ ስታዲየም ከአስቶንቪላ ጋር ካደረገው የውድድር አመቱ የመጨረሻ ጨዋታ በኋላ ደማቅ የሽኝት መርሃ ግብር ተዘካሂዷል።
ጋርድዮላ በስሜት ተውጦ እና እንባ እየተናነቀው "ይህን ያህል ፍቅር ለምን ሰጣችሁኝ?" በማለት ንግግሩን በጀመረበት ወቅት፣ በስታዲየሙ የታደሙት ደጋፊዎች በከፍተኛ ድምፅ ስሙን በመጥራትና የምስጋና መዝሙራትን በመዘመር ንግግሩን በተደጋጋሚ ያቋርጡት ነበር።
በስንብት ፕሮግራሙ ማጠቃለያ ላይም አሰልጣኙ ለክለቡ ደጋፊዎች ባስተላለፈው መልእክት "ወደየቤታችሁ ከመሄዳችሁ በፊት አንድ ነገር እንድናገር ፍቀዱልኝ፤ በቀጣዮቹ አመታት እዚህ ማንቸስተር ውስጥም ሆነ በማንኛውም የአውሮፓ ከተማ መንገድ ላይ ስታገኙኝ መጥታችሁ ሳታቅፉኝ እንዳታልፉ" ሲል የተማጸነ ሲሆን፣ ይህ ልብ የሚነካ መልእክቱ በአለም ዙሪያ በሚገኙ የክለቡ ደጋፊዎች ዘንድ በሰፊው እየተጋራ ይገኛል።
ፔፕ ጋርድዮላ በማንቸስተር ሲቲ ቆይታው ቡድኑን በ593 ጨዋታዎች ላይ መምራት የቻለ ሲሆን፣ የቀድሞውን አሰልጣኝ የሌዊስ ማክዶውልን የ592 ጨዋታዎች ክብረ ወሰን በመስበር በክለቡ ታሪክ ረጅም ጨዋታዎችን በመምራት ቀዳሚው መሆን ችሏል።
በእነዚህ ጨዋታዎች ውስጥም 416 ድሎችን ሲያስመዘግብ፣ 86 ጊዜ አቻ ወጥቶ በ91ዱ ደግሞ ሽንፈትን አስተናግዷል። በአጠቃላይ በአሰልጣኝነት ዘመኑ 20 ዋና ዋና ዋንጫዎችን ለክለቡ ያስገኘ ሲሆን፣ 5 ጊዜም የኢንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ የአመቱ ምርጥ አሰልጣኝ በመሆን መመረጡ ይታወሳል።
via ዮናታን አየለ
#manchestercity #pepguardiola #football #pep #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
Sponsored by
Surafel
17 days ago
#addisababa
ምክር ቤቱ ለቀብር የሚከፈልን ገንዘብ በ2,000 ብር ጭማሪ ማድረጉ ቅሬታ አስነሳ።
ም/ቤቱ በበኩሉ፣ የክፍያ ጭማሪው "የማህበረሰቡን ጫና የሚያቃልል ነው" ሲል ተደምጧል።
የአዲስ አበባ ከተማ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት "ለህፃናት ቀብር ይከፈል የነበረው 1000 ብር ወደ 2000 ብር" ከፍ ማድረጉን አስታውቋል።
"ለአዋቂ ቀብር ደግሞ ይከፈል የነበረው 2000 ብር ወደ 4000 ብር" ከፍ መደረጉን ያሳወቀ ሲሆን፣ በርካቶች ደግሞ ጭማሪው የኑሮ ውድነትን ያላገናዘበ በሚል ቅሬታ እያቀረቡ ናቸው።
ም/ቤቱ ግን፣ የተደረገው የዋጋ ጭማሪ "የማህበረሰቡን ጫና የሚያቃልል ነው" ብሏል። ይህን የተረዱ አስተያየት ሰጭዎች ደግሞ፣ እንዴት ነው የክፍያ ጭማሪ "ጫና የሚያቃልለው?" የሚል ጥያቄ እያቀረቡ ናቸው።
የክፍያ ጭሚሪው "ከዚህ በፊት በአገልግሎት ክፍያ ውስጥ የማይካተተውን የብሎኬት አቅርቦት የሚጨምር" መሆኑን ገልጾ፣ "ይህም ማህበሰቡ ለብሎኬት ግዢ ያወጣ የነበረውን ከ1200 ብር እስከ 1800 ብር ወጪን የሚያስቀር" ነው ብሏል።
በአዲሱ ጭማሪ "አንድ ተገልጋይ የሚከፍለው 4,000 የብሎኬት አቅርቦቱን ጨምሮ ሁሉንም የቀብር አገልግሎት የሚጨምር" መሆኑን ገልጿል። "አንድ የቀብር ስነ ስርዓት ለማከናውን በትንሹ እስከ 28 ብሎኬት እንደሚያስፈልግ" የጠቀሰው ም/ቤቱ፣ "ከአዲሱ ማሻሻያ በኋላ ይህንን አቅርቦት መጅሊስ የሚፈጽመው ይሆናል" ብሏል።
"በዋጋ ማሻሻያ ላይ በበጎ ፍቃደኛነት የጀናዛ እጥበትና ሽኝት በማድረግ ለቀብር አገልግሎት በሚመጡ ተቋማት ላይ ምንም ዓይነት የዋጋ ጭማሪ" አለመደረጉንም ባጋራው መረጃ አሳውቋል።
seledadotio
seledadotio
ምክር ቤቱ ለቀብር የሚከፈልን ገንዘብ በ2,000 ብር ጭማሪ ማድረጉ ቅሬታ አስነሳ።
ም/ቤቱ በበኩሉ፣ የክፍያ ጭማሪው "የማህበረሰቡን ጫና የሚያቃልል ነው" ሲል ተደምጧል።
የአዲስ አበባ ከተማ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት "ለህፃናት ቀብር ይከፈል የነበረው 1000 ብር ወደ 2000 ብር" ከፍ ማድረጉን አስታውቋል።
"ለአዋቂ ቀብር ደግሞ ይከፈል የነበረው 2000 ብር ወደ 4000 ብር" ከፍ መደረጉን ያሳወቀ ሲሆን፣ በርካቶች ደግሞ ጭማሪው የኑሮ ውድነትን ያላገናዘበ በሚል ቅሬታ እያቀረቡ ናቸው።
ም/ቤቱ ግን፣ የተደረገው የዋጋ ጭማሪ "የማህበረሰቡን ጫና የሚያቃልል ነው" ብሏል። ይህን የተረዱ አስተያየት ሰጭዎች ደግሞ፣ እንዴት ነው የክፍያ ጭማሪ "ጫና የሚያቃልለው?" የሚል ጥያቄ እያቀረቡ ናቸው።
የክፍያ ጭሚሪው "ከዚህ በፊት በአገልግሎት ክፍያ ውስጥ የማይካተተውን የብሎኬት አቅርቦት የሚጨምር" መሆኑን ገልጾ፣ "ይህም ማህበሰቡ ለብሎኬት ግዢ ያወጣ የነበረውን ከ1200 ብር እስከ 1800 ብር ወጪን የሚያስቀር" ነው ብሏል።
በአዲሱ ጭማሪ "አንድ ተገልጋይ የሚከፍለው 4,000 የብሎኬት አቅርቦቱን ጨምሮ ሁሉንም የቀብር አገልግሎት የሚጨምር" መሆኑን ገልጿል። "አንድ የቀብር ስነ ስርዓት ለማከናውን በትንሹ እስከ 28 ብሎኬት እንደሚያስፈልግ" የጠቀሰው ም/ቤቱ፣ "ከአዲሱ ማሻሻያ በኋላ ይህንን አቅርቦት መጅሊስ የሚፈጽመው ይሆናል" ብሏል።
"በዋጋ ማሻሻያ ላይ በበጎ ፍቃደኛነት የጀናዛ እጥበትና ሽኝት በማድረግ ለቀብር አገልግሎት በሚመጡ ተቋማት ላይ ምንም ዓይነት የዋጋ ጭማሪ" አለመደረጉንም ባጋራው መረጃ አሳውቋል።
seledadotio
seledadotio
17 days ago
ምክር ቤቱ ለቀብር የሚከፈልን ገንዘብ በ2,000 ብር ጭማሪ ማድረጉን አሳወቀ
#ethiopia | የአዲስ አበባ ከተማ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት "ለህፃናት ቀብር ይከፈል የነበረው 1000 ብር ወደ 2000 ብር" ከፍ ማድረጉን አስታውቋል።
"ለአዋቂ ቀብር ደግሞ ይከፈል የነበረው 2000 ብር ወደ 4000 ብር" ከፍ መደረጉን ያሳወቀ ሲሆን፣ በርካቶች ደግሞ ጭማሪው የኑሮ ውድነትን ያላገናዘበ በሚል ቅሬታ እያቀረቡ ናቸው።
ም/ቤቱ ግን፣ የተደረገው የዋጋ ጭማሪ "የማህበረሰቡን ጫና የሚያቃልል ነው" ብሏል። ይህን የተረዱ አስተያየት ሰጭዎች ደግሞ፣ እንዴት ነው የክፍያ ጭማሪ "ጫና የሚያቃልለው?" የሚል ጥያቄ እያቀረቡ ናቸው።
የክፍያ ጭሚሪው "ከዚህ በፊት በአገልግሎት ክፍያ ውስጥ የማይካተተውን የብሎኬት አቅርቦት የሚጨምር" መሆኑን ገልጾ፣ "ይህም ማህበሰቡ ለብሎኬት ግዢ ያወጣ የነበረውን ከ1200 ብር እስከ 1800 ብር ወጪን የሚያስቀር" ነው ብሏል።
በአዲሱ ጭማሪ "አንድ ተገልጋይ የሚከፍለው 4,000 የብሎኬት አቅርቦቱን ጨምሮ ሁሉንም የቀብር አገልግሎት የሚጨምር" መሆኑን ገልጿል። "አንድ የቀብር ስነ ስርዓት ለማከናውን በትንሹ እስከ 28 ብሎኬት እንደሚያስፈልግ" የጠቀሰው ም/ቤቱ፣ "ከአዲሱ ማሻሻያ በኋላ ይህንን አቅርቦት መጅሊስ የሚፈጽመው ይሆናል" ብሏል።
"በዋጋ ማሻሻያ ላይ በበጎ ፍቃደኛነት የጀናዛ እጥበትና ሽኝት በማድረግ ለቀብር አገልግሎት በሚመጡ ተቋማት ላይ ምንም ዓይነት የዋጋ ጭማሪ" አለመደረጉንም ባጋራው መረጃ አሳውቋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን) #getutemesgen #getu #thiqah #addisababa
#ethiopia | የአዲስ አበባ ከተማ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት "ለህፃናት ቀብር ይከፈል የነበረው 1000 ብር ወደ 2000 ብር" ከፍ ማድረጉን አስታውቋል።
"ለአዋቂ ቀብር ደግሞ ይከፈል የነበረው 2000 ብር ወደ 4000 ብር" ከፍ መደረጉን ያሳወቀ ሲሆን፣ በርካቶች ደግሞ ጭማሪው የኑሮ ውድነትን ያላገናዘበ በሚል ቅሬታ እያቀረቡ ናቸው።
ም/ቤቱ ግን፣ የተደረገው የዋጋ ጭማሪ "የማህበረሰቡን ጫና የሚያቃልል ነው" ብሏል። ይህን የተረዱ አስተያየት ሰጭዎች ደግሞ፣ እንዴት ነው የክፍያ ጭማሪ "ጫና የሚያቃልለው?" የሚል ጥያቄ እያቀረቡ ናቸው።
የክፍያ ጭሚሪው "ከዚህ በፊት በአገልግሎት ክፍያ ውስጥ የማይካተተውን የብሎኬት አቅርቦት የሚጨምር" መሆኑን ገልጾ፣ "ይህም ማህበሰቡ ለብሎኬት ግዢ ያወጣ የነበረውን ከ1200 ብር እስከ 1800 ብር ወጪን የሚያስቀር" ነው ብሏል።
በአዲሱ ጭማሪ "አንድ ተገልጋይ የሚከፍለው 4,000 የብሎኬት አቅርቦቱን ጨምሮ ሁሉንም የቀብር አገልግሎት የሚጨምር" መሆኑን ገልጿል። "አንድ የቀብር ስነ ስርዓት ለማከናውን በትንሹ እስከ 28 ብሎኬት እንደሚያስፈልግ" የጠቀሰው ም/ቤቱ፣ "ከአዲሱ ማሻሻያ በኋላ ይህንን አቅርቦት መጅሊስ የሚፈጽመው ይሆናል" ብሏል።
"በዋጋ ማሻሻያ ላይ በበጎ ፍቃደኛነት የጀናዛ እጥበትና ሽኝት በማድረግ ለቀብር አገልግሎት በሚመጡ ተቋማት ላይ ምንም ዓይነት የዋጋ ጭማሪ" አለመደረጉንም ባጋራው መረጃ አሳውቋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን) #getutemesgen #getu #thiqah #addisababa
21 days ago
የጀግናዋ አትሌት ሻምበል ባሻ የብርጓል መለሰ የቀብር ሥነ ሥርዓት ተፈጸመ
#ethiopia | በበርካታ ዓለም አቀፍ የውድድር መድረኮች የኢትዮጵያን ሰንደቅ ዓላማ ከፍ ስታደርግ የቆየችው ዝነኛዋ አትሌት ሻምበል ባሻ የብርጓል መለሰ የቀብር ሥነ ሥርዓት በመንበረ ፀባኦት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል በክብር ተፈጽሟል።
በመጋቢት ወር 1982 ዓ.ም በሰሜን ወሎ መቄት ወረዳ የተወለደችው አትሌቷ ከ1999 ዓ.ም ጀምሮ ወደ ሩጫው ዓለም በመግባት ስኬታማ ጉዞ ስታደርግ ቆይታለች።
በ2003 ዓ.ም የመከላከያ መቻል ስፖርት ክለብን በመቀላቀል በሀገር ውስጥና በዓለም አቀፍ ደረጃ በ10 ኪሎ ሜትር፣ በሀገር አቋራጭ እንዲሁም በማራቶን ውድድሮች በርካታ ድሎችን ለሀገሯና ለክለቧ አስመዝግባለች።
አትሌት የብርጓል መለሰ እ.ኤ.አ በ2015 በመላ አፍሪካ ጨዋታዎች የነሐስ ሜዳሊያ፣ በ2013 በዓለም ሀገር አቋራጭ ውድድር የብር ሜዳሊያ እንዲሁም በሂውስተን፣ በሻንጋይ፣ በፕራግ እና በሊዝበን ማራቶኖች አንደኛ በመውጣት ታላቅ ውጤት ያስመዘገበች ጀግና ነበረች።
አትሌቷ በካናዳ ለሚካሄደው የኦታዋ ማራቶን ዝግጅት እያደረገች በነበረበት ወቅት በደረሰባት ድንገተኛ የጤና እክል ግንቦት 4 ቀን 2018 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት ተለይታለች።
በዛሬው የቀብር ሥነ ሥርዓት ላይ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች፣ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን አመራሮች፣ የጦር ኃይሎች መኮንኖች፣ አትሌቶችና ቤተሰቦቿ በተገኙበት በመከላከያ የክብር ዘብ የታጀበ ሽኝት ተደርጎላታል።
አትሌት የብርጓል በትዳር አጋሯ አትሌት ወሰን ዘለቀና በሁለት ሕፃናት ልጆቿ እንዲሁም በሥራ ባልደረቦቿ ዘንድ በትሕትናዋና በአርአያነቷ የምትታወስ ታላቅ ስፖርተኛ ነበረች።
Getu Temesgen ( ጌጡ ተመስገን) ሚዲያና ኮሙኒኬሽንስ በጀግናዋ አትሌት ህልፈት የተሰማንን ጥልቅ ሐዘን እየገለጽን ለቤተሰቦ፤ ለአድናቂዎቿ መጽናናትን እንመኛለን።
#athletics #ethiopianathletes #yebrgualmelese #sportnews #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | በበርካታ ዓለም አቀፍ የውድድር መድረኮች የኢትዮጵያን ሰንደቅ ዓላማ ከፍ ስታደርግ የቆየችው ዝነኛዋ አትሌት ሻምበል ባሻ የብርጓል መለሰ የቀብር ሥነ ሥርዓት በመንበረ ፀባኦት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል በክብር ተፈጽሟል።
በመጋቢት ወር 1982 ዓ.ም በሰሜን ወሎ መቄት ወረዳ የተወለደችው አትሌቷ ከ1999 ዓ.ም ጀምሮ ወደ ሩጫው ዓለም በመግባት ስኬታማ ጉዞ ስታደርግ ቆይታለች።
በ2003 ዓ.ም የመከላከያ መቻል ስፖርት ክለብን በመቀላቀል በሀገር ውስጥና በዓለም አቀፍ ደረጃ በ10 ኪሎ ሜትር፣ በሀገር አቋራጭ እንዲሁም በማራቶን ውድድሮች በርካታ ድሎችን ለሀገሯና ለክለቧ አስመዝግባለች።
አትሌት የብርጓል መለሰ እ.ኤ.አ በ2015 በመላ አፍሪካ ጨዋታዎች የነሐስ ሜዳሊያ፣ በ2013 በዓለም ሀገር አቋራጭ ውድድር የብር ሜዳሊያ እንዲሁም በሂውስተን፣ በሻንጋይ፣ በፕራግ እና በሊዝበን ማራቶኖች አንደኛ በመውጣት ታላቅ ውጤት ያስመዘገበች ጀግና ነበረች።
አትሌቷ በካናዳ ለሚካሄደው የኦታዋ ማራቶን ዝግጅት እያደረገች በነበረበት ወቅት በደረሰባት ድንገተኛ የጤና እክል ግንቦት 4 ቀን 2018 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት ተለይታለች።
በዛሬው የቀብር ሥነ ሥርዓት ላይ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች፣ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን አመራሮች፣ የጦር ኃይሎች መኮንኖች፣ አትሌቶችና ቤተሰቦቿ በተገኙበት በመከላከያ የክብር ዘብ የታጀበ ሽኝት ተደርጎላታል።
አትሌት የብርጓል በትዳር አጋሯ አትሌት ወሰን ዘለቀና በሁለት ሕፃናት ልጆቿ እንዲሁም በሥራ ባልደረቦቿ ዘንድ በትሕትናዋና በአርአያነቷ የምትታወስ ታላቅ ስፖርተኛ ነበረች።
Getu Temesgen ( ጌጡ ተመስገን) ሚዲያና ኮሙኒኬሽንስ በጀግናዋ አትሌት ህልፈት የተሰማንን ጥልቅ ሐዘን እየገለጽን ለቤተሰቦ፤ ለአድናቂዎቿ መጽናናትን እንመኛለን።
#athletics #ethiopianathletes #yebrgualmelese #sportnews #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
22 days ago
የኮሚሽነር ዘገየ አስፋው የቀብር ሥነ ሥርዓት በቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ተከናወነ
#ethiopia | የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ኮሚሽነር የነበሩት የዘገየ አስፋው የሽኝት እና የቀብር ሥነ ሥርዓት በዛሬው ዕለት በቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ተፈጽሟል።
በዚሁ የቀብር ሥነ ሥርዓት ላይ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ፣ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አገኘሁ ተሻገር፣ የከንቲባ አዳነች አቤቤን ጨምሮ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች፣ የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን አመራሮች፣ የሟች ቤተሰቦችና ወዳጅ ዘመዶች በተገኙበት በክብር አርፈዋል።
ኮሚሽነር ዘገየ አስፋው በኢትዮጵያ የታሪክ ሂደት ውስጥ መሬት ለአራሹ እንዲሆን ከታገሉና አዋጁ እንዲጸድቅ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ካበረከቱ ቀዳሚ ግለሰቦች መካከል አንዱ ነበሩ።
ረጅም ዘመናቸውን በተለያዩ የመንግሥት የኃላፊነት እርከኖች ላይ በመመደብ ሀገራቸውን በታማኝነት ማገልገላቸው በሕይወት ታሪካቸው ላይ ተገልጿል።
ጋዜጠኛ እና ኮሚሽነር ዘገየ አስፋው በሕመም ምክንያት ሕክምና ሲከታተሉ ቆይተው በተወለዱ በ84 ዓመታቸው ግንቦት 3 ቀን 2018 ዓ.ም ማለፋቸው ይታወሳል።
#ሀገራዊምክክር #መሬትለአራሹ #ዘገየአስፋው #ኢትዮጵያ #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ኮሚሽነር የነበሩት የዘገየ አስፋው የሽኝት እና የቀብር ሥነ ሥርዓት በዛሬው ዕለት በቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ተፈጽሟል።
በዚሁ የቀብር ሥነ ሥርዓት ላይ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ፣ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አገኘሁ ተሻገር፣ የከንቲባ አዳነች አቤቤን ጨምሮ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች፣ የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን አመራሮች፣ የሟች ቤተሰቦችና ወዳጅ ዘመዶች በተገኙበት በክብር አርፈዋል።
ኮሚሽነር ዘገየ አስፋው በኢትዮጵያ የታሪክ ሂደት ውስጥ መሬት ለአራሹ እንዲሆን ከታገሉና አዋጁ እንዲጸድቅ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ካበረከቱ ቀዳሚ ግለሰቦች መካከል አንዱ ነበሩ።
ረጅም ዘመናቸውን በተለያዩ የመንግሥት የኃላፊነት እርከኖች ላይ በመመደብ ሀገራቸውን በታማኝነት ማገልገላቸው በሕይወት ታሪካቸው ላይ ተገልጿል።
ጋዜጠኛ እና ኮሚሽነር ዘገየ አስፋው በሕመም ምክንያት ሕክምና ሲከታተሉ ቆይተው በተወለዱ በ84 ዓመታቸው ግንቦት 3 ቀን 2018 ዓ.ም ማለፋቸው ይታወሳል።
#ሀገራዊምክክር #መሬትለአራሹ #ዘገየአስፋው #ኢትዮጵያ #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
24 days ago
አትሌቷ ዛሬ ማለዳ በጃንሜዳ ልምምድ እየሰራች ወድቃ ህይወቷ አለፈ
ዝነኛዋ የረጅም ርቀት ሯጭ የብርጓል መለሰ ዛሬ ግንቦት 4/2018 ዓ.ም ማለዳ በጃንሜዳ ልምምድ እየሰራች ሳለ በድንገት ወድቃ ነው ህይወቷ ማለፉ ተሰማ። አስክሬኗ በአሁኑ ሰዓት ለምርመራ ወደ ምኒልክ ሆስፒታል ተወስዷል።
እ.ኤ.አ በ2015 በኮንጎ ብራዛቪል በተካሄደው የመላው አፍሪካ ጨዋታዎች ሀገሯን ወክላ በግማሽ ማራቶን የነሃስ ማራቶን ያመጣችው አትሌቷ በዛው ዓመት በአሜሪካ ቺካጎ ማራቶን 2ኛ መውጣቷ ይታወሳል። በ2018 ደግሞ በቻይና ሻንጋይ ማራቶን 2:20.37 በሆነ ጊዜ ከሶስት ዓመታት በፊት በሀገሯ ልጅ ትዕግስት ቱፋ ተይዞ የነበረውን የቦታውን ሪከርድ (2:21.52) ከአንድ ደቂቃ በላይ በማሻሻል ማሸነፏ ይታወሳል።
በ2022 በፖርቹጋል ሊዝበን ግማሽ ማራቶን 1:07.18 በሆነ ጊዜ የቦታውን ሪከርድ ሰብራ አሸንፋለች። ባለፈው ዓመት በተካሄደው የፍራንክፈርት ማራቶን 2:2047 በሆነ ሰዓት 2ኛ ወጥታ ነበር። በ2018 በዱባይ ማራቶን 2:19.36 የገባችበት በማራቶን የግል ምርጥ ሰዓቷ ነው።
የፊታችን ግንቦት 16 በካናዳ በሚካሄደው የኦታዋ ማራቶን ከሚሳተፉት 12 ሴት ኢትዮጵያውያን አትሌቶች መካከል አንዷ የነበረችው ጀግናዋ አትሌት የብርጓል መለሰ ለአሸናፊነት የሚረዳትን ጠንካራ ልምምዷን በመስራት ላይ ሳለች ነው ዛሬ ማለዳ በድንገት ወድቃ ህይወቷ ያለፈው።
የብርጓል ባለትዳርና የሁለት ልጆች እናት ነበረች። አስክሬኗ ነገ ጠዋት ወደ ቤተሰቦቿ ወደ ወሎ ሽኝት ይደረግለታል።
ዝነኛዋ የረጅም ርቀት ሯጭ የብርጓል መለሰ ዛሬ ግንቦት 4/2018 ዓ.ም ማለዳ በጃንሜዳ ልምምድ እየሰራች ሳለ በድንገት ወድቃ ነው ህይወቷ ማለፉ ተሰማ። አስክሬኗ በአሁኑ ሰዓት ለምርመራ ወደ ምኒልክ ሆስፒታል ተወስዷል።
እ.ኤ.አ በ2015 በኮንጎ ብራዛቪል በተካሄደው የመላው አፍሪካ ጨዋታዎች ሀገሯን ወክላ በግማሽ ማራቶን የነሃስ ማራቶን ያመጣችው አትሌቷ በዛው ዓመት በአሜሪካ ቺካጎ ማራቶን 2ኛ መውጣቷ ይታወሳል። በ2018 ደግሞ በቻይና ሻንጋይ ማራቶን 2:20.37 በሆነ ጊዜ ከሶስት ዓመታት በፊት በሀገሯ ልጅ ትዕግስት ቱፋ ተይዞ የነበረውን የቦታውን ሪከርድ (2:21.52) ከአንድ ደቂቃ በላይ በማሻሻል ማሸነፏ ይታወሳል።
በ2022 በፖርቹጋል ሊዝበን ግማሽ ማራቶን 1:07.18 በሆነ ጊዜ የቦታውን ሪከርድ ሰብራ አሸንፋለች። ባለፈው ዓመት በተካሄደው የፍራንክፈርት ማራቶን 2:2047 በሆነ ሰዓት 2ኛ ወጥታ ነበር። በ2018 በዱባይ ማራቶን 2:19.36 የገባችበት በማራቶን የግል ምርጥ ሰዓቷ ነው።
የፊታችን ግንቦት 16 በካናዳ በሚካሄደው የኦታዋ ማራቶን ከሚሳተፉት 12 ሴት ኢትዮጵያውያን አትሌቶች መካከል አንዷ የነበረችው ጀግናዋ አትሌት የብርጓል መለሰ ለአሸናፊነት የሚረዳትን ጠንካራ ልምምዷን በመስራት ላይ ሳለች ነው ዛሬ ማለዳ በድንገት ወድቃ ህይወቷ ያለፈው።
የብርጓል ባለትዳርና የሁለት ልጆች እናት ነበረች። አስክሬኗ ነገ ጠዋት ወደ ቤተሰቦቿ ወደ ወሎ ሽኝት ይደረግለታል።
Sponsored by
Surafel
1 month ago
"በኢትዮጵያ ሰማይ ላይ
የሚበራው የሙዚቃ ኮከብ "
ከአለባቸው ደሳለኝ አበሻ (ለንደን)
#ethiopia | "ድምፁ የሀገር ሰንደቅ ዓላማ ያህል ክብር የሚሰጠው ጥላሁን ገሰሰ ለግማሽ ክፍለ ዘመን ያህል በኢትዮጵያ ሙዚቃ ውስጥ በነበረው ከፍተኛ አስተዋፅኦ የኢትዮጵያ ሙዚቃ ንጉሥ በሚል መጠሪያ ይታወቃል።
ለዚህ የጥበብ ሰው እንዲህ ያለ ጥልቅ እና ልብ የሚነካ ትዝታ ማዘጋጄት የሚቻለው የጥላሁን ገሰሰን ስራዎችን ብቻ ሳይሆን የእርሱን የውስጥ ማንነት ሠብዕናን ለጥበብ የነበረውን ፍቅር በሚገባ የተረዳ መሆን አለበት ።
ወይንም ደግሞ
የዚህን ታላቅ ምትሐተኛ ድምፃዊ የጥበብ ልክና የድምፅ ብቃት በአግባቡ ለመረዳት የእርሱን ግለ ታሪክ ብቻ ሳይሆን የኢትዮጵያን ዘመናዊ ሙዚቃ ታሪክና የጥላሁን ገሰሰን ሰፊ የሥራ ክምችቶች በጥልቀት መመርመር የግድ ይላል።
ምክኒያቱም
ጥላሁን ገሰሰ ማለት የኢትዮጵያ የ50 ዓመታት የደስታ የሐዘን የድልና የሽንፈት ታሪክ በድምፅ የተቀረጸበት "ሕያው ማህደር" ነው።
ጥላሁን ገሰሰ ድምፁን እንደፈለገ የማዘዝ Vocal Control ልዩ ተሰጥኦ ነበረው።
በጣም ረጅምና ከፍተኛ ድምፅ በሚጠይቁ High notes እንዲሁም በጣም ረጋ ያሉና ዝቅተኛ ድምፅ በሚሹ Low notes ዜማዎች ላይ እኩል ብቃት ነበረው።
የትንፋሽ ቁጥጥሩ ረጅም ስንኞችን ሳያቋርጥና ትንፋሽ ሳይጠረው የመጨረስ ችሎታው የሚደነቅ ነበር።
የጥላሁንን ስራዎች ስንመረምር በአንድ የሙዚቃ ዘውግ ብቻ ያልተገደበ መሆኑን እንረዳለን
ባህላዊና ዘመናዊ የባህል ሙዚቃዎችን ከዘመናዊ መሣሪያዎች ኦርኬስትራ ጋር አዋህዶ በማቅረብ ረገድ ቀዳሚ ነበር።
በጥላሁን ገሠሠ ድምፅ ያልተዘፈነ የሕይወት ክፍል የለም ማለት ይቻላል ።
ከጥልቅ የፍቅር ስሜት እስከ ሃገር ፍቅር ከማህበራዊ ትችት እስከ መንፈሳዊ መዝሙራት ድረስ የተፃፉ ግጥሞችና ዜማዎች የጥላሁንን ገሠሠን ድምፅ ለማድመቅ ሳይሆን ለመፈተን ጭምር የተዘጋጁ ይመስሉ ነበር።
በህይወት በቆየባቸው ሦስት የተለያዩ ሥርዓቶች በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ በደርግና በኢህአዴግ ውስጥ አልፏል። በእነዚህ ሁሉ ጊዜያት የሕዝብ ተወዳጅነቱን ጠብቆ መቆየቱ የሙዚቃ ሥራዎቹ ከፖለቲካዊ ለውጦች በላይ የሕዝብን የልብ ትርታ የሚነኩ መሆናቸውን ያሳያል።
ባጭሩ ጥላሁን ገሰሰ ለኢትዮጵያ ሙዚቃ ያለው አስተዋጽኦ ልክ እንደ አንድ ትልቅ "ኢንሳይክሎፒዲያ" ነው። አንዱን ገጽ አንብቦ ስለ መጽሐፉ ሙሉ ግንዛቤ ማግኘት እንደማይቻል ሁሉ
አንዱን ዘፈን አዳምጦ ስለ ጥላሁን ገሰሰ ማወቅ አይቻልም ።
እያንዳንዱ ዘፈኑ የራሱ የሆነ የቴክኒክ የታሪክና የስሜት ጥልቀት አለው።
ስለዚህ የጥላሁንን ታላቅነት ለመረዳት የኢትዮጵያን የሙዚቃ ጉዞ አብሮ መመርመር የግድ ነው ያልኩት ወድጄ አይደለም ።
ዘፈኖቹን ሲዘፍን በቃላት ብቻ ሳይሆን በፊቱ መግለጫና በሰውነት እንቅስቃሴው Body Language ጭምር ስሜቱን ለታዳሚው ያጋባ ነበር።
በተለይ የሐዘን ዜማዎችን ሲዘፍን አብሮ የሚያለቅስ የደስታ ሲሆን ደግሞ አብሮ ፈገግ የሚል ድምፃዊ ተዋና ጭምር ነበረ በዘፈኖቹ ውስጥ ሰውን ማክበርን ስራን መውደድንና አንድነትን ይሰብካል። ዘፈኑ የሰውን ልጅ ክብርና ማንነት የሚተነትን ድንቅ ስራ የሚሰራ ምትሀተኛ ድምፃዊ ነበር ።
ጥላሁን ገሰሰ በአንድ ወቅት በመድረክ ላይ እያለ በደረሰበት የጉሮሮ ህመም ምክንያት ለተወሰነ ጊዜ ድምፁ ተዘግቶ ነበር። ያን ጊዜ መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ተጨንቆና ፀልዮ ድምፁ ሲመለስለት ያደረገው የመጀመሪያ ኮንሰርት በዚያን ወቅት በኢትዮጵያ የሙዚቃ ታሪክ ውስጥ ከፍተኛውን የሰው ቁጥር ያስመዘገበ ነበር ። ይህ የሚያሳየው ሕዝቡ ለጥላሁን ያለው ፍቅር ከአንድ ድምፃዊ በላይ እንደ ቤተሰብ አባል የሚያየው መሆኑን ነው።
ስለ ፍቅር ብቻ ሳይሆን ስለ ሰው ልጅ ሕይወት ባዶነት የሚተርክ ጥልቅ ፍልስፍና ነበረው ።
ታዋቂው የኢትዮጵያ የሙዚቃ ንጉሥ ክቡር ዶክተር ጥላሁን ገሰሰ መስከረም 17 ቀን 1933 ዓ.ም አዲስ አበባ ውስጥ ተወልዶ ያደገው ግን በወሊሶ ከተማ ነው ።
ጥላሁን በ1950ዎቹ መጀመሪያ ላይ ወደ አዲስ አበባ በመምጣት መጀመሪያ ሐገር ፍቅር ቲያትርን በኋላም ዝነኛውን የክብር ዘበኛ የሙዚቃ ቡድንን ተቀላቅሎ ከዕንስት ፍቅር እስከ አገር ፍቅር ከባህላዊ እስከ ዘመናዊ ሙዚቃ በድምፃዊነት ከ400 በላይ ዘፈኖችን ተጫውቶ ልዩ ብቃቱን አስመስክሯል ።
ጥላሁን
ለኢትዮጵያ ሙዚቃ ላበረከተው ወደር የለሽ አስተዋጽኦ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የክብር ዶክትሬት ዲግሪ ተሰጥቶታል። ጥላሁን ገሠሠ ከዚህ ዓለም በሞት የተለየው
በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር ሚያዝያ 11 ቀን 2001 ዓ.ም. የፋሲካ እለት ሲሆን በድንገተኛ የልብ ህመም ምክንያት አርፎ በቅድስት ሥላሴ ካቴድራል የቀብር ሥነሥርዓቱ ተፈጽሟል።
የክቡር ዶክተር ጥላሁን ገሰሰ ማረፍ መላውን የኢትዮጵያ ሕዝብና የጥበብ አፍቃሪወችን በከፍተኛ ድንጋጤና ሃዘን ውስጥ ጥሎ የነበረ ክስተት ነው። በወቅቱ በጋዜጦች በሬዲዮና በቴሌቪዥን የተላለፉት መልዕክቶች ጥላሁን ለሀገሩ ያለውን ትልቅ ቦታ የሚያንፀባርቁ ነበሩ።
በአዲስ አበባ ከተማ የነበሩ የታክሲ አሽከርካሪዎች ሐዘን ፈፅሞ የማይረሳ ነበረ ።
ለጥላሁን ገሰሰ ክብር ሲሉ ለቀናት ጥቁር ጨርቅ በታክሲዎቻቸው ላይ አስረውና የእርሱን ሙዚቃ ብቻ ከፍተው በማጫወት ሃዘናቸውን ገልፀውለታል።
የጥላሁን ገሰሰ ሞት በሀገር ውስጥ ብቻ ሳይሆን በዓለም አቀፍ ደረጃም ትኩረት አግኝቶ ነበር።
ታዋቂው ደራሲ ሎሬት ጸጋዬ ገብረመድህንም
እንዲህ አሉ ።
"ጥላሁን የኢትዮጵያ ሕዝብ የጋራ ድምፅ ነው። እርሱ ሲዘፍን መላው ኢትዮጵያዊ ራሱን ያዳምጣል።"
ድምፃዊ ማህሙድ አህመድ"ጥላሁን ለእኛ ለድምፃውያን መምህራችን ብቻ ሳይሆን የሙዚቃው ዓምድ ነበር። ጥላሁን ሞተ ማለት የኢትዮጵያ ሙዚቃ ግማሽ አካሉን አጣ ማለት ነው።" ሲል ቁጭቱን ገልፀዋል ።
በቀብር ሥነ ሥርዓቱ ላይ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ አዲስ አበባውያን ወደ አደባባይ በመውጣት "ንጉሥ አይሞትም" እያሉ ሲያለቅሱ እንደነበር በታሪክ ተመዝግቧል።
ይህም አንድ ድምፃዊ በሀገር ደረጃ ያለውን ክብርና ተሰሚነት ያሳየ ትልቅ ክስተት ነበር።
አንድ የልብ አድናቂው የሆነ ሠው በማህበራዊ ሚዲያ እንዲህ ብሎ ፅፎት አንብቢያለሁ ።
" በእርግጥም ጥላሁን በድምፁ ተአምር የመስራት አቅም ነበረው። ድምፁ ተስፋ የቆረጠውን የሚያፅናና የታመመውን የሚፈውስና የራቀውን የሚያቀራርብ
ስለነበረ ድምፁ ተቀርፆ ስለቀረ ቢሞትም ስንናፍቀው እናገኘዋለን ስናዝን እናለቅስበታለን ሀገራችን ስትጠራ በእሱ ድምፅ አቤት ብለን ለአንድነቷ እንቆማለን" በማለት ጥላሁንን ገልፆት ነበር ።
ሌላው የቅርብ ጓደኛው የጥበብ ሰው ደበበ እሸቱ ነው
"ጥላሁን በሕይወት ዘመኑ ሁሉ ለሀገሩ የዘመረ በችግር ጊዜ ደግሞ ድምፁን ለድሆች የሰጠ
ታላቅ ሰው ነው።
የሞተው በስጋ ቢሆንም በዜማው ቅላፄና በግጥም ስንኞች ውስጥ "ዘላለማዊ" ሆኖ ተተክሏል።
እንዲህ ያለ ድምፅ ዓለማችን በአንድ ዘመን አንዴ ብቻ የምትለግሰን ስጦታ ነው "
ሲል ምስክርነቱን ገልጿል።
በእርግጥም ጥላሁን የዘመናዊ ሙዚቃችን "ፊደል" እና "መዝገበ ቃላት" ሆኖ አልፏል። ከድምፅ ጥራት በላይ የዜማ አጣጣልና ስሜትን የመግለጽ ጥበቡ ማንም የማይደረስበት ከፍታ ላይ ስለነበር በአንድ አባባል ብቻ ጥላሁንን መግለፅ አይቻልም።
እሱ ባለብዙ ምዕራፍና ተነቦ የማይጠገብ ባለ ብዙ ገጽ ድርሳን ነው !
ጥላሁን ለሙያው ብቻ ሳይሆን ለሰው ልጅ የነበረው ሰብአዊ ክብርም ድንቅ ነበር። ረሀብ ሲመጣ በዜማው የሚማፀን ሀገር ስትቸገር አጥንቴም ይከስከስ ብሎ የሚቆም እና ለሰው ልጅ ፍቅር ቅድሚያ የሚሰጥ የጥበብ ሰው ነው ። ባጭሩ ጥላሁን ገሠሠ ማለት ለኢትዮጵያውያን የድምፅ ብቻ ሳይሆን የህሊና ምስክር ነው።
ዛሬም ድረስ ስሙ ሲነሳ አብሮ የሚነሳው ክብሩ ትህትናውና
ያ የማይደገም ማንነቱ ነው።
ጥላሁን ገሠሠን የመሠለ ታላቅ ሰው የኢትዮጵያ ዘመናዊ ሙዚቃን የአዋለደ ብለን ብንገልፀው ተገቢ ይመስለኛል ከጥላሁን ገሠሠ ስራዎች መካከል ይህማ ተአምር ነው የሚያሰኜኘኝ ሁልጊዜ ብሰማቸው አዲስ የሚሆኑብኝ ብዙ ዘፈኖች ቢኖሩትም "እዩት ስትናፍቀኝ ከአጠገቤ እያለች" የሚለው ስንኝ ሲነሳ ግን የጥላሁንን ድምፅና ያንን የሚመስጥ አዘፋፈኑን አብሮ የመስማት ያህል ይመስጠኛል እዩት ስትናፍቀኝ ከአጠገቤ እያለች
እንዲህ ያለው መውደድ ለወሬም አይመች ! የሚለው ግጥም የፍቅርን ረቂቅነትና የማይመረመር ባህሪ በአጭር ቃላት የገለጸበት ድንቅ ስራው ነው።
ጥላሁን ለዚህ ዘፈን የሰጠው እረዥም ትንፋሽና በመድረክ ላይ ቆሞ የአይን አስተያየቱ የልዩ ተሰጥኦው መገለጫዎቹ ናቸው።
የሠው ልጅ ናፍቆት ብዙውን ጊዜ ትዝታው የሚመጣው ሰው ሲርቅ ነው። ነገር ግን ጥላሁን አጠገቤ እያለች ናፈቀችኝ ማለቱ ፍቅር ከስጋዊ መገኘት በላይ የሆነ የነፍስ ጥማት መሆኑን ስጋ አልብሶ አሳይቶናል ።
ይህ ለወሬ የማይመች ቃላት የማይገልፁት ጥልቅ ስሜት ነው ። ይህንንም በዚያ ረጅም ትንፋሽ ነፍስን በሚያከነፍ ድምፁ ሲያዜመው እውነቱን በውስጣችን ውስጥ እናገኘዋለን።
ጥላሁን ሲዘፍን ትንፋሹን የሚጠቀምበት መንገድ እና ስሜቱን በድምፅ ቀለም የመቀየር ችሎታው ምትሐተኛ ያሰኘዋል። ያንን የናፍቆት ጣጣ በገዛ ራሱ ላይ አድርጎ ሲያዜመው አድማጩ የራሱ ህመም አድርጎ እንዲቀበለው የማድረግ ልዩ ኃይል ነበረው።
ጥላሁን ገሠሠ በስጋ ቢለየንም በኢትዮጵያውያን ልብ ውስጥ ግን አሁንም ንጉሥ ነው።
ትውልድ ያልፋል ጥላሁን ግን ይኖራል።
ሙዚቃ ይቀየራል የጥላሁን ስራዎች ግን ሁልጊዜ አዲስ ናቸው።
ሰላም ሲጠፋ ጥላሁን ፍቅር ይላል ሀገር ስትናፈቅ ጥላሁን ሀገሬ ይላል።
ጥላሁን ገሠሠ በድምፁ ብቻ ሳይሆን ለፍቅር በሰጠው ክብርን በገለፀበት ጥበብ የኢትዮጵያ የዘላለም የፍቅር አምባሳደር ነው።
እንዲህ ያለው የጥበብ ሰው የፍቅርን ኃያልነት በእሱ ስራዎች ውስጥ ስንመለከት በእርግጥም ፍቅር ስሜት ብቻ አይደለም የሚለውን ሃሳብ በጥላሁን ዜማዎች ውስጥ ሙሉ ማረጋገጫውን እናገኛለን ጥላሁን ገሠሠ የፍቅርን ሌላኛውን ገጽታ ቁርጠኝነትንና ክብርን ያሳየበት ድንቅ ስራው ነው። ከላይ እንደገለፅኩት ፍቅር ራስን አሳልፎ መስጠት ነው
እዚህ ዘፈን ላይ ደግሞ ፍቅር ሁለትዮሽ መረዳዳት መሆኑን ይነግረናል።
ቻልኩት ፍቅር ለብቻዬ !!
ይህ አገላለጽ በጣም የሚቆረቁር ነው። ፍቅር እንደ አንድ ሸክም ሆኖ አንደኛው ወገን ብቻውን ሲሸከመው የሚሰማውን ድካም ያሳያል። "ለብቻዬ መሸከም ሰልችቶኛል" የሚል የልብ ጩኸት አለበት። ፍቅር የሁለት ሰው ቅኝት እንጂ የአንድ ሰው ብቸኛ ትግል መሆን እንደሌለበት ያስገነዝበናል።
ስለ ፍቅር አልገባሽም
እዚህ ጋር ጥላሁን ፍቅር ማለት ዝም ብሎ አብሮ መሆን ሳይሆን ጥልቅ የሆነ
ሚስጥር ወይም ትርጉም እንዳለው ይገልጻል። ግዴለሽነት እና ችላ ማለት ፍቅርን የሚገድሉ መርዞች መሆናቸውን በምሬት ይናገራል።
አትምጪ ይቅር ሲል ደግሞ የክብር ውሳኔውን ያሳውቃል ።
ፍቅር ስሜት ብቻ አለመሆኑን ያረጋግጣል። አንድ ሰው በጥልቅ እያፈቀረ ግን ክብሩ ሲነካ ወይም ምላሽ ሲያጣ ይቅር ብሎ የመወሰን አቅም ሊኖረው እንደሚገባ ያሳያል።
ፍቅር መስዋዕትነት ቢሆንም ዋጋ በማይሰጠው ቦታ ላይ ግን ራስን ማዳንና ይቅር ማለትም የፍቅር አካል ነው። የሚገርመው ደግሞ ጥላሁን ይህነን ዘፈን ሲዘፍነው በቁጣና በቁጭት ሳይሆን በጥልቅ ሀዘንና በከበረ ስሜት ነው። ያንን አትምጪ ይቅር የሚለውን ቃል ሲያወጣው ውስጡ እየፈለጋት ግን መከባበር የሌለበት ፍቅር እንደማይፀና አውቆ በቁርጠኝነት ሲናገረው ይታየናል።
ከላይ እንዳነሳሁት አትምጪ ይቅር የሚለው ስንኝ የቁርጠኝነትና የክብር ገጹ ሲሆን ሌላው ደግሞ የፍቅርን ንፁህ መስዋዕትነትና ትህትና የሚያሳይ ድንቅ ምዕራፍ ነው።
እነዚህ ስንኞች ውስጥ የምናያቸው የጥላሁን ድርሳናት
እኔ ልሁን እንጂ የማልጠቅም እርካሽ ! የሚለው አገላለፅ በፍቅር ውስጥ ያለን ፍጹም ትህትና ያሳያል። ራሱን ዝቅ አድርጎ የሚወዳትን ሰው ግን ከፍ ያደርጋታል። ይህ እኔነት ጠፍቶ አንቺነት የነገሰበት የፍቅር ጫፍ ነው።
ከህይወቴ አብልጨ ሲል
ራስን አሳልፎ የመስጠት
ፍልስፍና በተግባር የሚያሳይ ታአምር ነው። ለሰው ልጅ ከህይወቱ በላይ ምንም የለውም ነገር ግን ፍቅር ያንን ውድ ህይወት እንኳ ከአንቺ አያበልጠውም ብሎ እንዲያምን ያደርገዋል።
ፍቅር ለሰላምና ለደስታ ብቻ ሳይሆን ለችግርና ለፈተናም ዝግጁ መሆኑን ይነግረናል።
መከራና ስቃይ ይቆየኝ ግዴለኝም
የሚወደው ሰው ደህንነትና ሰላም እስካለ ድረስ እሱ በራሱ ላይ ለሚመጣው መከራ ግድ የለውም። ይህ ነው እንግዲህ ፍቅርን ተአምር የሚያሰኘው እግዜር በጥበቡ ከአንቺ ብቻ አይለየኝ የሚለው ቃል ፍቅር በሰው ጥረት ብቻ ሳይሆን በመለኮታዊ ጥበብና ፈቃድ የሚፀና መሆኑን የሚያሳይ የልብ ፆሎት በመሆኑ መንፈሳዊ ልመና ይጨምርበታል ።
ታዲያ የዚህን ድምፃዊ ተአምራዊ ተቃርኖዎችን ስንመለከት
ጥላሁንን ልዩ የሚያደርገው በአንድ በኩል አትምጪ ይቅር ብሎ በክብር የመወሰን አቅም በሌላ በኩል ደግሞ ከህይወቴ አብልጨ እወድሻለሁ ብሎ ራስን የመስጠት ርህራሄ አብሮት መኖሩ ነው።
እነዚህ ሁለት ተቃራኒ የሚመስሉ ግን ጥልቅ የሆኑ የፍቅር ገጾች ናቸው።
ጥላሁን እነዚህን ሁሉ ስሜቶች በድምፅ ቀለም እየቀያየረ ሲያቀርባቸው ድምፁ ብቻ ሳይሆን ነፍሱ አብራ የምትዘፍን ይመስላል።
እንዲህ ያለውን ከህይወት በላይ የመውደድ ስሜት በዚህ ዘመን በብዛት እናገኘዋለን ብሎ ማሰብ የዋህነት ነው። ምክኒያቱም
የጥላሁንን ጥበብ ከመዝፈን ባለፈ ወደ መፍጠር ደረጃ ከፍ ያደርገዋል።
ለምን ቢባል ጥላሁን ገሠሠ ዜማንና ግጥምን ሲያዋህድ የሚፈጠረው ነገር ተራ ሙዚቃ አይደለም ይልቁንም ያልተጠኑ ምስጢራዊ ተሰጥኦዎች ያሉበት ይመስላል
ብዙ አድናቂወቹ እንደ ሚስማሙበት ጥላሁን ገሠሠ ሲዘፍን ፍቅር ረቂቅ ሃሳብ መሆኑ ቀርቶ የሚዳሰስ የሚታይና የሚሰማ አካል ይኖረዋል።
ቃላቶቹ ከአፉ ሲወጡ ሕይወት ይዘራሉ ያፈቀረው ሰው ቁስሉ ይታየናል የናፈቀው ሰው ትንፋሹ ይሰማናል። ይህ ደግሞ በቴክኒክ ብቻ የሚመጣ ሳይሆን ከነፍስ የሚመነጭ ምትሃት በመሆኑ ፍቅር እንደ ሰው ቆሞ እንዲሄድ የማድረግ ጥልቅና ረቂቅ
ጥበብ ያለው ድምፃዊ መሆኑ ነው ።
ብዙዎቻችን ውስጣችን ያለውን ጥልቅ ፍቅር በቃላት መግለፅ ያቅተናል። ጥላሁን ግን ያንን መግለፅ ያቃተንን ስሜት ሰርቆ ወስዶ በዜማ አቅልጦ ወርቅ አርጎ መልሶ ለእኛው ይሰጠናል።
እኔንም እንዲህ ነው የሚሰማኝ! እንድንል ያደርገናል። ይህ ተሰጥኦው ነው ፍቅርን ስጋ ለብሶ ቆሞ እንዲሄድ የሚያደርገው።
ሌላው የጥላሁን ገሰሰ ድምፅ ሁለንተናዊ ድምፅ መሆኑ ነው። እድሜ ጾታ ወይም የትምህርት ደረጃ አይወስነውም። ህፃኑም አዋቂውም የተማረውም ያልተማረውም በዜማው ውስጥ የራሳቸውን ታሪክ ያገኛሉ።
ይህ ደግሞ ጥላሁን የሰው ልጅን የጋራ የፍቅር ህመም ጠንቅቆ እንደሚያውቅ ማሳያ ነው።
የጥላሁን ድምፅ በሳይንስ አልተጠናም እንጂ በውስጡ ትልቅ የፍቅር ላብራቶሪ ነበረው ማለት ይቻላል።
ግጥሙን ይቀበላል ጥሬ እቃ !
በድምፅ ቀለሙ ያዋህደዋል ሂደት !
በመጨረሻም ሕያው ፍቅርን ለዓለም ያበረክታል ውጤት !! በዚህ ምክኒያት
ጥላሁን ገሠሠ ሞቶም በሰዎች ልብ ውስጥ እንዲነግስ አድርጎታል :: ምክንያቱም የፈጠራቸው የፍቅር አካላት ዛሬም በየቤታችን በየመኪናችንና በየልባችን ውስጥ ቆመው እየሄዱ ነው።
ይህ የእውነት ተአምረኛ ተሰጥኦው ነው። ዛሬ ባለው ዘመናዊ የሙዚቃ ኢንዱስትሪ ውስጥ እንዲህ ያለውን መንፈሳዊ ጥልቅነት ማግኘት እጅግ ብርቅ ሆኗል። ከእንስት ፍቅር ወጥተን ጥላሁንን ወደ ሐገር ፍቅር ስንመነዝረው የቆመበት ከፍታው ላይ እስከ አሁን ማንም ....ማንም አልደረሠበት ። በዚህ አጋጣሚ
በህይወቴ ዘመኔ በአይኔ ያየሁትን ምስክርነት ባቀርበው ደስ ይለኛል ጥለሁን ገሠሠ ከታሪክ መዝገብ በላይ የሆነ የአንድን ሕዝብ ማንነትና ወኔ የቀሰቀሰ የመንፈስ ተአምር ነው የምነግራችሁ ።
ጊዜው 1974 አስመራ የቀይ ኮኮብ ዘመቻ አሉላ አባ ነጋ አዳራሽ ውስጥ ይመስለኛል ።
ጥላሁን ገሠሠ ጋሻና ጎራዴ ይዞ የአርበኛ ልብስ ለብሶ አጥንቴም ይከስከስ ደሜም ይፍሠስላት
ግን ሐገሬን ጭራሽ አይደፍራትም ጠላት
እያለ መድረኩን ሞልቶት ብቅ ሲል ከባለስልጣን እሰከ ተራው ተመልካች ከመቀመጫው ተነስቶ በመቆም በማያቋርጥ ጩህትና ጭብጨባ ያጅቡታል ።
ጥላሁን ገሠሠ በዚያ ቅጽበት የዘፈነውን ብቻ ሳይሆን የኖረውንና የታሪካችንን ድምፅ ሆኖ ተመለከትኩት ።
ጥላሁን በህዝብ ጭብጨባና ጬህት ታጅቦ መድረኩ ላይ ሲንጎራደድ አዳራሹ ድብልቅልቁ ወጣ ።
ያን... ምህታታት የተሞላበት ትርኢት ስመለከት
የአድዋ ጀግኖች መቃብር ከፍተው የተነሱ ይመስል ነበር።
ማለቴ ጥላሁን በድምፁ ብቻ ሳይሆን በቆይታው ጊዜን የማቆም ወይም ታሪክን የመቀስቀስ ኃይል እንደነበረው የመመልከት ዕድል አግኝቻለሁ ።
ጥላሁንን በዚያች ቅፅበት
በሕይወት እያለ ሐውልቱን አቁሞ አዳራሹ ውስጥ ታሪኩን ፅፎት ወጣ ።
በእርግጥ ሐውልት የማይናገርና የማይሰማ የድንጋይ ምስል ነው ጥላሁን ግን በሕይወት ያለ የሚተነፍስ የሚዘፍንና የሚራመድ የኢትዮጵያዊነት ሐውልት ነበር።
ዛሬም ቢሆን ስራዎቹ ያንን ግርማ ሞገስና ያንን ሐውልታዊ ፅናት እያስታወሱኝ እስከእለተ ሞቴ ድረስ ልረሳው አልችልም እንዲህ አይነት ድርጊት
ፍቅር ስሜት ብቻ አይደለም ራስን አሳልፎ መስጠት ነው በጥላሁን ገሰሰ የሀገር ፍቅር ዜማዎች ውስጥ ኢትዮጵያን ደጋግመን እናያታለን
አጥንቴም ይከስከስ ደሜም ይፍሰስላት የሚለው ቃል ዛሬም ድረስ ፍፁም ....ፍፁም መስዋዕትነት ነው።
ሀገሩን እንደ ሚወዳት እናት ወይም ሚስት አድርጎ ለሷ ክብር መሞትን እንደ ትልቅ ፀጋ መቁጠር ከፍ ያለ የፍቅር ደረጃ መግለጫ ነው።
ተመልካቹ በሙሉ ሳይቀመጥ ከሁለት ጊዜ በላይ ይደገም እያለ መጠየቁ ጥላሁን ድምፃዊ ብቻ ሳይሆን መሪ መሆኑን በአንድ ዜማ ሕዝብን የማስተሳሰር በአንድ ወኔ በጋራ የማቆም ተአምራዊ አቅሙን አረጋግጨበታለሁ ።
በዚያች ቅፅብት ቲያትር ቤቱ በጩሄትና በጭብጨባ ቀውጢ ሲሆን ጥላሁን ገሠሠ በድምፁ ብቻ የጠላትን ምሽግ የሚያፈርስ ጀግና መስሎ ነበር የሚታየው ።
ምንም እንኳን ዛሬ በሞት ቢለየንም ያ አስመራ ላይ የተመለከትኩት የሐገር ፍቅር ስሜት ሐውልት ሆኖ በልቤ ውስጥ ተቀርፆ ቆሟል።
ጥላሁን ገሰሰን ልዩ የሚደርገው ሌላው መገለጫው
ለፍቅር ሲዘፍን የፍቅር ሐውልት
ለሀገር ሲዘፍን የጀግንነት ሐውልት
ለሰው ልጅ ክብር ሲዘፍን የሰብአዊነት ሐውልት ነው!
ለዚህ ስኬት ደግሞ ከጥላሁን ድምፅ ጀርባ የነበሩት የወርቃማው ዘመን ታላላቅ የጥበብ ሰዎች ገጣሚያንና የዜማ አቀናባሪዎች ሚና ከፍተኛ እንደነበር ምስክሩ ታሪክና ሕዝቡ ነው።
ጥላሁን ገሰሰ ግጥምና ዜማን
ከነጄነራል አማኑኤል አብርሃም
ሻምበል አፈወርቅ ዮሐንስ
ነጋሽ ገብረማርያም
ተስፋዬ አበበ አየለ ማሞ ሳህሌ ደጋጎ ክፍሌ አቦቸር ከመሳሰሉት የክብር ዘበኛ እና የፖሊስ ኦርኬስትራዎች
ተቀብሎ ሲያንቆረቁረው ሙዚቃው ከድምፅ አልፎ የሚዳሰስ ሕያው መንፈስ የመሆን አቅም ነበረው።
ዛሬ ላይ ሆኜ ያንን ትርኢት ሳስታውሰው ጥላሁን ለኢትዮጵያ ሙዚቃና ለኢትዮጵያዊነት ያለው ትርጉም ምን ያህል ጥልቅ ስሜት እንደሆነ አሁን ድረስ እንደ ህልም ይታየኛል ።
ያኔ መድረክ ላይ ሲወጣ የነበረው ግርማ ሞገስና ድምፁ ሲስተጋባ የተሰማኝ ስሜት ዛሬም ድረስ ዘፈኑን ስሰማው "የጦር ፊታውራሪ" የነበረ ጀግና ያህል ትዝ ይለኛል !!
ጥላሁን በመድረክ ላይ የነበረውን የበላይነት እና የሕዝብን ስሜት የመምራት ብቃቱን በሚገባ የመግለፅ አቅም ነበረው ።
ጥላሁን ዝም ብሎ ድምፃዊ ሳይሆን በዜማው የታጠቀ የሀገር መከታ ወታደርም ሆኖ እንደነበረ ማሳያ ነው ።
ለዚህ ነው የጥላሁን ገሠሠ የሀገር ፍቅር ዜማዎች ከጊዜና ከቦታ በላይ የሆኑ ናቸው የሚባሉት ። ለዚህም ነው ዛሬ ላይ ሆነን ስንሰማው የዛሬ 130 ዓመት በፊት የተነገረውን የዳግማዊ ምኒልክን የክተት አዋጅ የሚመስለን ።
ይህ የሚያሳየው ደግሞ ጥላሁን የኢትዮጵያን ታሪክ ኩራትና ነፃነት በድምፅ ቀርጾ ትውልድ እንዲወርሰው ማድረጉን ነው።
ወዳጆቼ
ስለ ጥላሁን ገሠሠ የሀገር ፍቅር ስሜት ስንናገር እነዚህ ሶስት መሰረታዊ እውነታዎች ጎልተው ይታያኛል ።
የቁርጠኝነት ድምፁን ስናደዳምጠው ጥላሁን "አገሬን" ሲል ዝም ብሎ ስም አይጠራም ለሀገሩ የሚሞትላትና የሚሰዋላት መሆኑን በቃናው ውስጥ ይሰማል። አጥንቴም ይከስከስ የሚለው ስንኝ ለዚህ ትልቅ ማሳያ ነው።
ጥላሁን ለሀገር ሲዘፍን መላው ኢትዮጵያዊ በአንድነት ቆሞ ፊታውራሪዬ ብሎ እንዲከተለው ያደርጋል።
ይህ ደግሞ በታሪካችን ውስጥ የታየ ትልቅ የጥበብ ተጽዕኖ ነው።
ከ130 ዓመት በፊት የነበረውን የአድዋ ጀግንነት ዛሬ ላለው ትውልድ በስሜት አገናኝቶ ማቅረብ የሚችለው እንደ ጥላሁን ያለ "የታሪክ ድልድይና የታሪክ ባለአደራ" ሲኖር ብቻ ነው።
እንኳንስ ደስታየን የሰውነቴን ሠው
እንኳን ነፃነቴን ፀጋ ክብሬን ትቸው
በናት አገር ምድር በሚያውቀኝ በማውቀው ...
ስቃይ መከራዬን ከአንችው ዘንድ ያድርገው ። የሚለው
ጥላሁን ለኢትዮጵያ የነበረውን ፍቅር ከምንም በላይ የሚያሳይ ነው። ከባዕድ አገር ደስታ ይልቅ የሀገሩን መከራ የመረጠበት የሞቱ አጋጣሚ ደግሞ ለሀገሩ ያለውን ፍቅር በደሙ ያረጋገጠበት ታላቅ ክስተት ነው ።
ጥላሁን ከአሜሪካ ተነስቶ ለፋሲካ በዓል ወደ ሀገሩ መግባቱና በዚያው ዕለት ማረፉ፣ "በሀገሬ አፈር ልቀበር" የሚለውን ጥልቅ የኢትዮጵያዊያን ምኞት የፈጸመበት ነው ይህ ቀረኝ የማይል የሚያሰኘው እስከ መጨረሻው ትንፋሹ ድረስ ከሀገሩና ከሕዝቡ ጋር መቆየቱ ነው ።
ሲሞት መላው የአዲስ አበባ ሕዝብ በነቂስ ወጥቶ አስከሬኑን ሲሸኜው ጥላሁን ለሕዝቡ የሰጠውን ፍቅር ሕዝቡ በታላቅ ክብር የመለሰለት መሆኑን ቅድስት ስላሴ ቤተክርስቲያን ህያው ምስክር ናት ። ያ ለቅሶ የአንድ ድምፃዊ ስንብት ሳይሆን የኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጅና የልብ ትርታ ሽኝት ነበር።
ጥላሁን በሕይወቱና በሞቱ ሀገርን መውደድ ማለት ትርጉሙን እስከ ሞት ድረስ መታመንን አረጋግጦበታል።
ሰውን መውደድ ! አብሮ ማልቀስና መቆም ሙያን መውደድ እስከ መጨረሻዋ ትንፋሽ ድረስ መዘመር ለኢትዮጵያዊያን ከድምፃዊነት በላይ የአንድነት ምልክት መሆን ነው።
እኔ በዓይኔ ያየሁትን በልቤ የሰነድኩትን ይህንን ታሪክ ለሚቀጥለው ትውልድ ሊተላለፍ የሚገባው የፍቅርና የሀገር አምልኮ ትልቅ ትምህርት ይሆናል ብየ ሳዘጋጀው ጥላሁን ገሠሠ
ትንፋሼ ተቀርፆ ይቀመጥ ማልቀሻ ይህ ነው የሞትኩለት የኔ ማስታወሻ
ታሪኬ ነው ድምፄ በማለት ያንጎራጎረው ሙዚቃ ከፍቼ እያዳመጥኩ ነበር።
ይህ ስንኝ ጥላሁን ገሠሠ አስቀድሞ በድምፁ የህይወቱ ታሪክ የሞቱ ማስታወሻ እና የሀገሩ ውበት መገለጫ እንደሚሆን ተረድቶት የተጫወተው ነበር ማለት ይቻላል ። ጥላሁን በጥቁርና ነጭ ወረቀት ላይ የሰፈረ ኑዛዜ ሳይሆን የተውልን በህይወት ቆሞ በዜማ የተናዘዘው ድንቅ ስንብት ነበረ ።
እነዚህ ስንኞች የጥላሁንን የጥበብ ክብርና ትህትና ሲገለፅበት እያዳመጥኩት ነበር ይህን ታሪክ የፃፍኩት ።
ወዳጃቸ
የጥላሁን ገሠሠ ድምፅ ዝም ብሎ የአየር ንዝረት አይደለም፤ ማንነቱ፣ ታሪኩና ለሀገሩ የከፈለው መስዋዕትነት ነው። በጩኸት መኖሬን ማለቱ ለሀገርና ለፍቅር ሲል ድምፁን እስከ መጨረሻው የጥገታ ነጥብ ድረስ መጠቀሙንና ለዚህም መሞቱን ያሳያል።
ድምፄን ሰምቶ ያዝናል ለረገፈው አፅሜ ሲል
እጅግ ልብ ይነካል !
ጥላሁን በከፍታው ላይ ሆኖ እንኳ ያስቀየምኩት ቢኖር ብሎ ይቅርታን ይጠይቃል። የሞተውን አፅሙን ሳይሆን የቀረውን ድምፁን ሰምተው ሰዎች እንዲያዝኑለትና ይቅር እንዲሉት መመኘቱ የሰው ልጅነቱንይቅርታና ትህትናውን
ፍርጥ አድርጎ ያሳያል።
ጥላሁን ገሠሠ በድምፁና በህይወቱ የሰራው ትልቁ ስራ ፍቅርንና ኢትዮጵያዊነትን ማዳን ነበር። ጥላሁን ከቀላል ስሜትነት አልፎ ሕይወት መስዋዕትነትና የሀገር ፍቅር ጥግ መሆኑን በሚገባ አስገንዝቦናል።ጥበብ እንዴት የአንድን ሕዝብ ወኔና ማንነት እንደምትቀርፅ ጥላሁን ትልቅ ማሳያ ነው።
ፍቅር ተግባር ነው ፍቅር ዝም ብሎ የሚሰማን ስሜት ሳይሆን እንደ ጥላሁን ዜማዎች ራስን አሳልፎ እስከ መስጠት የሚደርስ ውሳኔ መሆኑን መረዳት ከባድ አይደለም ።
ጥላሁን ገሰሰ የሚዘፈነው ለጆሮ ብቻ ሳይሆን ለህሊና እና ለነፍስ ጭምር ይመስለኛል ።
ጥላሁን ዛሬ በሥጋ ቢለየንም ታሪኬ ነው ድምፄ ብሎ እንደተናዘዘው ሁሉ ዛሬም በየልባችን ውስጥ ንጉሥ ሆኖ ይኖራል።እሱ ለሀገር ብቻ ሳይሆን ለሰው ልጅ ስቃይ የሚራራ የህሊና ድምፅ ነበረው።
የሀገር ፍቅር ለአፈርና ለሰንደቅ ዓላማ የሚከፈል የአጥንትና የደም መስዋዕትነት ሲሆን ጥላሁን ገሠሠ በስጋ ቢለየንም ያ በሕይወት ያለ ሐውልት ግን በዜማዎቹ ውስጥ ሁሌም አዲስ ሆኖ ይኖራል።
ባጭሩ የጥላሁን መሞት ዝም ብሎ የአንድ ድምፃዊ ማለፍ ብቻ አልነበረም የአንድ ዘመን መቋጫ የአንድ ትልቅ ተስፋ መደብዘዝ እና በኢትዮጵያ ሰማይ ላይ የሚበራው የሙዚቃ ኮከብ ወድቆ ሲሰበር
ሰማይ ባዶ የሆነ ያህል ተሰምቶናል።
ጥላሁን ገሠሠ በደስታ ጊዜ አብሮን የሚጨፍር በጦርነት ጊዜ ፊታውራሪ ሆኖ የሚያዘምት በረሃብና በችግር ጊዜ ደግሞ አብሮን የሚላቀስ የሕዝብ ልብ ነበር ።
ጥላሁንን ከአቅም በላይ ያደረገው ይሄው ሁለንተናዊነቱ ነው። ለፍቅር ለሀገርና ለሰብአዊነት የነበረው ጽናት እሱ ሞቶም እንዲኖር አድርጎታል።
የጥላሁን ገሠሠ ዘፈኖች "ኢትዮጵያዊ ስነ-ሰብዕና" የሚባል የፍልስፍና ዘርፍ ቢኖር የዛ ዘርፍ ዋና መማሪያ መፅሐፍ ይሆኑ ነበር ።ብቻ
የጥላሁንገሰሰ ሕይወት ልክ እንደ አንድ የተቀደሰ መፅሐፍ በመሆኑ እራሡ ከፍቶ እራሱ ዘግቶት አልፏል ።
ለዚህ ታላቅ ድምፃዊ በተወለደበት ከተማ አዲስ አበባ ላይ ዘላለማዊ ምልክት ሆኖ እንዲቀመጥ ሐውልቱ ስለቆመለት ደስታዬ ወደር የለውም ።
ነፍስ ይማር !!
የሚበራው የሙዚቃ ኮከብ "
ከአለባቸው ደሳለኝ አበሻ (ለንደን)
#ethiopia | "ድምፁ የሀገር ሰንደቅ ዓላማ ያህል ክብር የሚሰጠው ጥላሁን ገሰሰ ለግማሽ ክፍለ ዘመን ያህል በኢትዮጵያ ሙዚቃ ውስጥ በነበረው ከፍተኛ አስተዋፅኦ የኢትዮጵያ ሙዚቃ ንጉሥ በሚል መጠሪያ ይታወቃል።
ለዚህ የጥበብ ሰው እንዲህ ያለ ጥልቅ እና ልብ የሚነካ ትዝታ ማዘጋጄት የሚቻለው የጥላሁን ገሰሰን ስራዎችን ብቻ ሳይሆን የእርሱን የውስጥ ማንነት ሠብዕናን ለጥበብ የነበረውን ፍቅር በሚገባ የተረዳ መሆን አለበት ።
ወይንም ደግሞ
የዚህን ታላቅ ምትሐተኛ ድምፃዊ የጥበብ ልክና የድምፅ ብቃት በአግባቡ ለመረዳት የእርሱን ግለ ታሪክ ብቻ ሳይሆን የኢትዮጵያን ዘመናዊ ሙዚቃ ታሪክና የጥላሁን ገሰሰን ሰፊ የሥራ ክምችቶች በጥልቀት መመርመር የግድ ይላል።
ምክኒያቱም
ጥላሁን ገሰሰ ማለት የኢትዮጵያ የ50 ዓመታት የደስታ የሐዘን የድልና የሽንፈት ታሪክ በድምፅ የተቀረጸበት "ሕያው ማህደር" ነው።
ጥላሁን ገሰሰ ድምፁን እንደፈለገ የማዘዝ Vocal Control ልዩ ተሰጥኦ ነበረው።
በጣም ረጅምና ከፍተኛ ድምፅ በሚጠይቁ High notes እንዲሁም በጣም ረጋ ያሉና ዝቅተኛ ድምፅ በሚሹ Low notes ዜማዎች ላይ እኩል ብቃት ነበረው።
የትንፋሽ ቁጥጥሩ ረጅም ስንኞችን ሳያቋርጥና ትንፋሽ ሳይጠረው የመጨረስ ችሎታው የሚደነቅ ነበር።
የጥላሁንን ስራዎች ስንመረምር በአንድ የሙዚቃ ዘውግ ብቻ ያልተገደበ መሆኑን እንረዳለን
ባህላዊና ዘመናዊ የባህል ሙዚቃዎችን ከዘመናዊ መሣሪያዎች ኦርኬስትራ ጋር አዋህዶ በማቅረብ ረገድ ቀዳሚ ነበር።
በጥላሁን ገሠሠ ድምፅ ያልተዘፈነ የሕይወት ክፍል የለም ማለት ይቻላል ።
ከጥልቅ የፍቅር ስሜት እስከ ሃገር ፍቅር ከማህበራዊ ትችት እስከ መንፈሳዊ መዝሙራት ድረስ የተፃፉ ግጥሞችና ዜማዎች የጥላሁንን ገሠሠን ድምፅ ለማድመቅ ሳይሆን ለመፈተን ጭምር የተዘጋጁ ይመስሉ ነበር።
በህይወት በቆየባቸው ሦስት የተለያዩ ሥርዓቶች በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ በደርግና በኢህአዴግ ውስጥ አልፏል። በእነዚህ ሁሉ ጊዜያት የሕዝብ ተወዳጅነቱን ጠብቆ መቆየቱ የሙዚቃ ሥራዎቹ ከፖለቲካዊ ለውጦች በላይ የሕዝብን የልብ ትርታ የሚነኩ መሆናቸውን ያሳያል።
ባጭሩ ጥላሁን ገሰሰ ለኢትዮጵያ ሙዚቃ ያለው አስተዋጽኦ ልክ እንደ አንድ ትልቅ "ኢንሳይክሎፒዲያ" ነው። አንዱን ገጽ አንብቦ ስለ መጽሐፉ ሙሉ ግንዛቤ ማግኘት እንደማይቻል ሁሉ
አንዱን ዘፈን አዳምጦ ስለ ጥላሁን ገሰሰ ማወቅ አይቻልም ።
እያንዳንዱ ዘፈኑ የራሱ የሆነ የቴክኒክ የታሪክና የስሜት ጥልቀት አለው።
ስለዚህ የጥላሁንን ታላቅነት ለመረዳት የኢትዮጵያን የሙዚቃ ጉዞ አብሮ መመርመር የግድ ነው ያልኩት ወድጄ አይደለም ።
ዘፈኖቹን ሲዘፍን በቃላት ብቻ ሳይሆን በፊቱ መግለጫና በሰውነት እንቅስቃሴው Body Language ጭምር ስሜቱን ለታዳሚው ያጋባ ነበር።
በተለይ የሐዘን ዜማዎችን ሲዘፍን አብሮ የሚያለቅስ የደስታ ሲሆን ደግሞ አብሮ ፈገግ የሚል ድምፃዊ ተዋና ጭምር ነበረ በዘፈኖቹ ውስጥ ሰውን ማክበርን ስራን መውደድንና አንድነትን ይሰብካል። ዘፈኑ የሰውን ልጅ ክብርና ማንነት የሚተነትን ድንቅ ስራ የሚሰራ ምትሀተኛ ድምፃዊ ነበር ።
ጥላሁን ገሰሰ በአንድ ወቅት በመድረክ ላይ እያለ በደረሰበት የጉሮሮ ህመም ምክንያት ለተወሰነ ጊዜ ድምፁ ተዘግቶ ነበር። ያን ጊዜ መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ተጨንቆና ፀልዮ ድምፁ ሲመለስለት ያደረገው የመጀመሪያ ኮንሰርት በዚያን ወቅት በኢትዮጵያ የሙዚቃ ታሪክ ውስጥ ከፍተኛውን የሰው ቁጥር ያስመዘገበ ነበር ። ይህ የሚያሳየው ሕዝቡ ለጥላሁን ያለው ፍቅር ከአንድ ድምፃዊ በላይ እንደ ቤተሰብ አባል የሚያየው መሆኑን ነው።
ስለ ፍቅር ብቻ ሳይሆን ስለ ሰው ልጅ ሕይወት ባዶነት የሚተርክ ጥልቅ ፍልስፍና ነበረው ።
ታዋቂው የኢትዮጵያ የሙዚቃ ንጉሥ ክቡር ዶክተር ጥላሁን ገሰሰ መስከረም 17 ቀን 1933 ዓ.ም አዲስ አበባ ውስጥ ተወልዶ ያደገው ግን በወሊሶ ከተማ ነው ።
ጥላሁን በ1950ዎቹ መጀመሪያ ላይ ወደ አዲስ አበባ በመምጣት መጀመሪያ ሐገር ፍቅር ቲያትርን በኋላም ዝነኛውን የክብር ዘበኛ የሙዚቃ ቡድንን ተቀላቅሎ ከዕንስት ፍቅር እስከ አገር ፍቅር ከባህላዊ እስከ ዘመናዊ ሙዚቃ በድምፃዊነት ከ400 በላይ ዘፈኖችን ተጫውቶ ልዩ ብቃቱን አስመስክሯል ።
ጥላሁን
ለኢትዮጵያ ሙዚቃ ላበረከተው ወደር የለሽ አስተዋጽኦ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የክብር ዶክትሬት ዲግሪ ተሰጥቶታል። ጥላሁን ገሠሠ ከዚህ ዓለም በሞት የተለየው
በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር ሚያዝያ 11 ቀን 2001 ዓ.ም. የፋሲካ እለት ሲሆን በድንገተኛ የልብ ህመም ምክንያት አርፎ በቅድስት ሥላሴ ካቴድራል የቀብር ሥነሥርዓቱ ተፈጽሟል።
የክቡር ዶክተር ጥላሁን ገሰሰ ማረፍ መላውን የኢትዮጵያ ሕዝብና የጥበብ አፍቃሪወችን በከፍተኛ ድንጋጤና ሃዘን ውስጥ ጥሎ የነበረ ክስተት ነው። በወቅቱ በጋዜጦች በሬዲዮና በቴሌቪዥን የተላለፉት መልዕክቶች ጥላሁን ለሀገሩ ያለውን ትልቅ ቦታ የሚያንፀባርቁ ነበሩ።
በአዲስ አበባ ከተማ የነበሩ የታክሲ አሽከርካሪዎች ሐዘን ፈፅሞ የማይረሳ ነበረ ።
ለጥላሁን ገሰሰ ክብር ሲሉ ለቀናት ጥቁር ጨርቅ በታክሲዎቻቸው ላይ አስረውና የእርሱን ሙዚቃ ብቻ ከፍተው በማጫወት ሃዘናቸውን ገልፀውለታል።
የጥላሁን ገሰሰ ሞት በሀገር ውስጥ ብቻ ሳይሆን በዓለም አቀፍ ደረጃም ትኩረት አግኝቶ ነበር።
ታዋቂው ደራሲ ሎሬት ጸጋዬ ገብረመድህንም
እንዲህ አሉ ።
"ጥላሁን የኢትዮጵያ ሕዝብ የጋራ ድምፅ ነው። እርሱ ሲዘፍን መላው ኢትዮጵያዊ ራሱን ያዳምጣል።"
ድምፃዊ ማህሙድ አህመድ"ጥላሁን ለእኛ ለድምፃውያን መምህራችን ብቻ ሳይሆን የሙዚቃው ዓምድ ነበር። ጥላሁን ሞተ ማለት የኢትዮጵያ ሙዚቃ ግማሽ አካሉን አጣ ማለት ነው።" ሲል ቁጭቱን ገልፀዋል ።
በቀብር ሥነ ሥርዓቱ ላይ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ አዲስ አበባውያን ወደ አደባባይ በመውጣት "ንጉሥ አይሞትም" እያሉ ሲያለቅሱ እንደነበር በታሪክ ተመዝግቧል።
ይህም አንድ ድምፃዊ በሀገር ደረጃ ያለውን ክብርና ተሰሚነት ያሳየ ትልቅ ክስተት ነበር።
አንድ የልብ አድናቂው የሆነ ሠው በማህበራዊ ሚዲያ እንዲህ ብሎ ፅፎት አንብቢያለሁ ።
" በእርግጥም ጥላሁን በድምፁ ተአምር የመስራት አቅም ነበረው። ድምፁ ተስፋ የቆረጠውን የሚያፅናና የታመመውን የሚፈውስና የራቀውን የሚያቀራርብ
ስለነበረ ድምፁ ተቀርፆ ስለቀረ ቢሞትም ስንናፍቀው እናገኘዋለን ስናዝን እናለቅስበታለን ሀገራችን ስትጠራ በእሱ ድምፅ አቤት ብለን ለአንድነቷ እንቆማለን" በማለት ጥላሁንን ገልፆት ነበር ።
ሌላው የቅርብ ጓደኛው የጥበብ ሰው ደበበ እሸቱ ነው
"ጥላሁን በሕይወት ዘመኑ ሁሉ ለሀገሩ የዘመረ በችግር ጊዜ ደግሞ ድምፁን ለድሆች የሰጠ
ታላቅ ሰው ነው።
የሞተው በስጋ ቢሆንም በዜማው ቅላፄና በግጥም ስንኞች ውስጥ "ዘላለማዊ" ሆኖ ተተክሏል።
እንዲህ ያለ ድምፅ ዓለማችን በአንድ ዘመን አንዴ ብቻ የምትለግሰን ስጦታ ነው "
ሲል ምስክርነቱን ገልጿል።
በእርግጥም ጥላሁን የዘመናዊ ሙዚቃችን "ፊደል" እና "መዝገበ ቃላት" ሆኖ አልፏል። ከድምፅ ጥራት በላይ የዜማ አጣጣልና ስሜትን የመግለጽ ጥበቡ ማንም የማይደረስበት ከፍታ ላይ ስለነበር በአንድ አባባል ብቻ ጥላሁንን መግለፅ አይቻልም።
እሱ ባለብዙ ምዕራፍና ተነቦ የማይጠገብ ባለ ብዙ ገጽ ድርሳን ነው !
ጥላሁን ለሙያው ብቻ ሳይሆን ለሰው ልጅ የነበረው ሰብአዊ ክብርም ድንቅ ነበር። ረሀብ ሲመጣ በዜማው የሚማፀን ሀገር ስትቸገር አጥንቴም ይከስከስ ብሎ የሚቆም እና ለሰው ልጅ ፍቅር ቅድሚያ የሚሰጥ የጥበብ ሰው ነው ። ባጭሩ ጥላሁን ገሠሠ ማለት ለኢትዮጵያውያን የድምፅ ብቻ ሳይሆን የህሊና ምስክር ነው።
ዛሬም ድረስ ስሙ ሲነሳ አብሮ የሚነሳው ክብሩ ትህትናውና
ያ የማይደገም ማንነቱ ነው።
ጥላሁን ገሠሠን የመሠለ ታላቅ ሰው የኢትዮጵያ ዘመናዊ ሙዚቃን የአዋለደ ብለን ብንገልፀው ተገቢ ይመስለኛል ከጥላሁን ገሠሠ ስራዎች መካከል ይህማ ተአምር ነው የሚያሰኜኘኝ ሁልጊዜ ብሰማቸው አዲስ የሚሆኑብኝ ብዙ ዘፈኖች ቢኖሩትም "እዩት ስትናፍቀኝ ከአጠገቤ እያለች" የሚለው ስንኝ ሲነሳ ግን የጥላሁንን ድምፅና ያንን የሚመስጥ አዘፋፈኑን አብሮ የመስማት ያህል ይመስጠኛል እዩት ስትናፍቀኝ ከአጠገቤ እያለች
እንዲህ ያለው መውደድ ለወሬም አይመች ! የሚለው ግጥም የፍቅርን ረቂቅነትና የማይመረመር ባህሪ በአጭር ቃላት የገለጸበት ድንቅ ስራው ነው።
ጥላሁን ለዚህ ዘፈን የሰጠው እረዥም ትንፋሽና በመድረክ ላይ ቆሞ የአይን አስተያየቱ የልዩ ተሰጥኦው መገለጫዎቹ ናቸው።
የሠው ልጅ ናፍቆት ብዙውን ጊዜ ትዝታው የሚመጣው ሰው ሲርቅ ነው። ነገር ግን ጥላሁን አጠገቤ እያለች ናፈቀችኝ ማለቱ ፍቅር ከስጋዊ መገኘት በላይ የሆነ የነፍስ ጥማት መሆኑን ስጋ አልብሶ አሳይቶናል ።
ይህ ለወሬ የማይመች ቃላት የማይገልፁት ጥልቅ ስሜት ነው ። ይህንንም በዚያ ረጅም ትንፋሽ ነፍስን በሚያከነፍ ድምፁ ሲያዜመው እውነቱን በውስጣችን ውስጥ እናገኘዋለን።
ጥላሁን ሲዘፍን ትንፋሹን የሚጠቀምበት መንገድ እና ስሜቱን በድምፅ ቀለም የመቀየር ችሎታው ምትሐተኛ ያሰኘዋል። ያንን የናፍቆት ጣጣ በገዛ ራሱ ላይ አድርጎ ሲያዜመው አድማጩ የራሱ ህመም አድርጎ እንዲቀበለው የማድረግ ልዩ ኃይል ነበረው።
ጥላሁን ገሠሠ በስጋ ቢለየንም በኢትዮጵያውያን ልብ ውስጥ ግን አሁንም ንጉሥ ነው።
ትውልድ ያልፋል ጥላሁን ግን ይኖራል።
ሙዚቃ ይቀየራል የጥላሁን ስራዎች ግን ሁልጊዜ አዲስ ናቸው።
ሰላም ሲጠፋ ጥላሁን ፍቅር ይላል ሀገር ስትናፈቅ ጥላሁን ሀገሬ ይላል።
ጥላሁን ገሠሠ በድምፁ ብቻ ሳይሆን ለፍቅር በሰጠው ክብርን በገለፀበት ጥበብ የኢትዮጵያ የዘላለም የፍቅር አምባሳደር ነው።
እንዲህ ያለው የጥበብ ሰው የፍቅርን ኃያልነት በእሱ ስራዎች ውስጥ ስንመለከት በእርግጥም ፍቅር ስሜት ብቻ አይደለም የሚለውን ሃሳብ በጥላሁን ዜማዎች ውስጥ ሙሉ ማረጋገጫውን እናገኛለን ጥላሁን ገሠሠ የፍቅርን ሌላኛውን ገጽታ ቁርጠኝነትንና ክብርን ያሳየበት ድንቅ ስራው ነው። ከላይ እንደገለፅኩት ፍቅር ራስን አሳልፎ መስጠት ነው
እዚህ ዘፈን ላይ ደግሞ ፍቅር ሁለትዮሽ መረዳዳት መሆኑን ይነግረናል።
ቻልኩት ፍቅር ለብቻዬ !!
ይህ አገላለጽ በጣም የሚቆረቁር ነው። ፍቅር እንደ አንድ ሸክም ሆኖ አንደኛው ወገን ብቻውን ሲሸከመው የሚሰማውን ድካም ያሳያል። "ለብቻዬ መሸከም ሰልችቶኛል" የሚል የልብ ጩኸት አለበት። ፍቅር የሁለት ሰው ቅኝት እንጂ የአንድ ሰው ብቸኛ ትግል መሆን እንደሌለበት ያስገነዝበናል።
ስለ ፍቅር አልገባሽም
እዚህ ጋር ጥላሁን ፍቅር ማለት ዝም ብሎ አብሮ መሆን ሳይሆን ጥልቅ የሆነ
ሚስጥር ወይም ትርጉም እንዳለው ይገልጻል። ግዴለሽነት እና ችላ ማለት ፍቅርን የሚገድሉ መርዞች መሆናቸውን በምሬት ይናገራል።
አትምጪ ይቅር ሲል ደግሞ የክብር ውሳኔውን ያሳውቃል ።
ፍቅር ስሜት ብቻ አለመሆኑን ያረጋግጣል። አንድ ሰው በጥልቅ እያፈቀረ ግን ክብሩ ሲነካ ወይም ምላሽ ሲያጣ ይቅር ብሎ የመወሰን አቅም ሊኖረው እንደሚገባ ያሳያል።
ፍቅር መስዋዕትነት ቢሆንም ዋጋ በማይሰጠው ቦታ ላይ ግን ራስን ማዳንና ይቅር ማለትም የፍቅር አካል ነው። የሚገርመው ደግሞ ጥላሁን ይህነን ዘፈን ሲዘፍነው በቁጣና በቁጭት ሳይሆን በጥልቅ ሀዘንና በከበረ ስሜት ነው። ያንን አትምጪ ይቅር የሚለውን ቃል ሲያወጣው ውስጡ እየፈለጋት ግን መከባበር የሌለበት ፍቅር እንደማይፀና አውቆ በቁርጠኝነት ሲናገረው ይታየናል።
ከላይ እንዳነሳሁት አትምጪ ይቅር የሚለው ስንኝ የቁርጠኝነትና የክብር ገጹ ሲሆን ሌላው ደግሞ የፍቅርን ንፁህ መስዋዕትነትና ትህትና የሚያሳይ ድንቅ ምዕራፍ ነው።
እነዚህ ስንኞች ውስጥ የምናያቸው የጥላሁን ድርሳናት
እኔ ልሁን እንጂ የማልጠቅም እርካሽ ! የሚለው አገላለፅ በፍቅር ውስጥ ያለን ፍጹም ትህትና ያሳያል። ራሱን ዝቅ አድርጎ የሚወዳትን ሰው ግን ከፍ ያደርጋታል። ይህ እኔነት ጠፍቶ አንቺነት የነገሰበት የፍቅር ጫፍ ነው።
ከህይወቴ አብልጨ ሲል
ራስን አሳልፎ የመስጠት
ፍልስፍና በተግባር የሚያሳይ ታአምር ነው። ለሰው ልጅ ከህይወቱ በላይ ምንም የለውም ነገር ግን ፍቅር ያንን ውድ ህይወት እንኳ ከአንቺ አያበልጠውም ብሎ እንዲያምን ያደርገዋል።
ፍቅር ለሰላምና ለደስታ ብቻ ሳይሆን ለችግርና ለፈተናም ዝግጁ መሆኑን ይነግረናል።
መከራና ስቃይ ይቆየኝ ግዴለኝም
የሚወደው ሰው ደህንነትና ሰላም እስካለ ድረስ እሱ በራሱ ላይ ለሚመጣው መከራ ግድ የለውም። ይህ ነው እንግዲህ ፍቅርን ተአምር የሚያሰኘው እግዜር በጥበቡ ከአንቺ ብቻ አይለየኝ የሚለው ቃል ፍቅር በሰው ጥረት ብቻ ሳይሆን በመለኮታዊ ጥበብና ፈቃድ የሚፀና መሆኑን የሚያሳይ የልብ ፆሎት በመሆኑ መንፈሳዊ ልመና ይጨምርበታል ።
ታዲያ የዚህን ድምፃዊ ተአምራዊ ተቃርኖዎችን ስንመለከት
ጥላሁንን ልዩ የሚያደርገው በአንድ በኩል አትምጪ ይቅር ብሎ በክብር የመወሰን አቅም በሌላ በኩል ደግሞ ከህይወቴ አብልጨ እወድሻለሁ ብሎ ራስን የመስጠት ርህራሄ አብሮት መኖሩ ነው።
እነዚህ ሁለት ተቃራኒ የሚመስሉ ግን ጥልቅ የሆኑ የፍቅር ገጾች ናቸው።
ጥላሁን እነዚህን ሁሉ ስሜቶች በድምፅ ቀለም እየቀያየረ ሲያቀርባቸው ድምፁ ብቻ ሳይሆን ነፍሱ አብራ የምትዘፍን ይመስላል።
እንዲህ ያለውን ከህይወት በላይ የመውደድ ስሜት በዚህ ዘመን በብዛት እናገኘዋለን ብሎ ማሰብ የዋህነት ነው። ምክኒያቱም
የጥላሁንን ጥበብ ከመዝፈን ባለፈ ወደ መፍጠር ደረጃ ከፍ ያደርገዋል።
ለምን ቢባል ጥላሁን ገሠሠ ዜማንና ግጥምን ሲያዋህድ የሚፈጠረው ነገር ተራ ሙዚቃ አይደለም ይልቁንም ያልተጠኑ ምስጢራዊ ተሰጥኦዎች ያሉበት ይመስላል
ብዙ አድናቂወቹ እንደ ሚስማሙበት ጥላሁን ገሠሠ ሲዘፍን ፍቅር ረቂቅ ሃሳብ መሆኑ ቀርቶ የሚዳሰስ የሚታይና የሚሰማ አካል ይኖረዋል።
ቃላቶቹ ከአፉ ሲወጡ ሕይወት ይዘራሉ ያፈቀረው ሰው ቁስሉ ይታየናል የናፈቀው ሰው ትንፋሹ ይሰማናል። ይህ ደግሞ በቴክኒክ ብቻ የሚመጣ ሳይሆን ከነፍስ የሚመነጭ ምትሃት በመሆኑ ፍቅር እንደ ሰው ቆሞ እንዲሄድ የማድረግ ጥልቅና ረቂቅ
ጥበብ ያለው ድምፃዊ መሆኑ ነው ።
ብዙዎቻችን ውስጣችን ያለውን ጥልቅ ፍቅር በቃላት መግለፅ ያቅተናል። ጥላሁን ግን ያንን መግለፅ ያቃተንን ስሜት ሰርቆ ወስዶ በዜማ አቅልጦ ወርቅ አርጎ መልሶ ለእኛው ይሰጠናል።
እኔንም እንዲህ ነው የሚሰማኝ! እንድንል ያደርገናል። ይህ ተሰጥኦው ነው ፍቅርን ስጋ ለብሶ ቆሞ እንዲሄድ የሚያደርገው።
ሌላው የጥላሁን ገሰሰ ድምፅ ሁለንተናዊ ድምፅ መሆኑ ነው። እድሜ ጾታ ወይም የትምህርት ደረጃ አይወስነውም። ህፃኑም አዋቂውም የተማረውም ያልተማረውም በዜማው ውስጥ የራሳቸውን ታሪክ ያገኛሉ።
ይህ ደግሞ ጥላሁን የሰው ልጅን የጋራ የፍቅር ህመም ጠንቅቆ እንደሚያውቅ ማሳያ ነው።
የጥላሁን ድምፅ በሳይንስ አልተጠናም እንጂ በውስጡ ትልቅ የፍቅር ላብራቶሪ ነበረው ማለት ይቻላል።
ግጥሙን ይቀበላል ጥሬ እቃ !
በድምፅ ቀለሙ ያዋህደዋል ሂደት !
በመጨረሻም ሕያው ፍቅርን ለዓለም ያበረክታል ውጤት !! በዚህ ምክኒያት
ጥላሁን ገሠሠ ሞቶም በሰዎች ልብ ውስጥ እንዲነግስ አድርጎታል :: ምክንያቱም የፈጠራቸው የፍቅር አካላት ዛሬም በየቤታችን በየመኪናችንና በየልባችን ውስጥ ቆመው እየሄዱ ነው።
ይህ የእውነት ተአምረኛ ተሰጥኦው ነው። ዛሬ ባለው ዘመናዊ የሙዚቃ ኢንዱስትሪ ውስጥ እንዲህ ያለውን መንፈሳዊ ጥልቅነት ማግኘት እጅግ ብርቅ ሆኗል። ከእንስት ፍቅር ወጥተን ጥላሁንን ወደ ሐገር ፍቅር ስንመነዝረው የቆመበት ከፍታው ላይ እስከ አሁን ማንም ....ማንም አልደረሠበት ። በዚህ አጋጣሚ
በህይወቴ ዘመኔ በአይኔ ያየሁትን ምስክርነት ባቀርበው ደስ ይለኛል ጥለሁን ገሠሠ ከታሪክ መዝገብ በላይ የሆነ የአንድን ሕዝብ ማንነትና ወኔ የቀሰቀሰ የመንፈስ ተአምር ነው የምነግራችሁ ።
ጊዜው 1974 አስመራ የቀይ ኮኮብ ዘመቻ አሉላ አባ ነጋ አዳራሽ ውስጥ ይመስለኛል ።
ጥላሁን ገሠሠ ጋሻና ጎራዴ ይዞ የአርበኛ ልብስ ለብሶ አጥንቴም ይከስከስ ደሜም ይፍሠስላት
ግን ሐገሬን ጭራሽ አይደፍራትም ጠላት
እያለ መድረኩን ሞልቶት ብቅ ሲል ከባለስልጣን እሰከ ተራው ተመልካች ከመቀመጫው ተነስቶ በመቆም በማያቋርጥ ጩህትና ጭብጨባ ያጅቡታል ።
ጥላሁን ገሠሠ በዚያ ቅጽበት የዘፈነውን ብቻ ሳይሆን የኖረውንና የታሪካችንን ድምፅ ሆኖ ተመለከትኩት ።
ጥላሁን በህዝብ ጭብጨባና ጬህት ታጅቦ መድረኩ ላይ ሲንጎራደድ አዳራሹ ድብልቅልቁ ወጣ ።
ያን... ምህታታት የተሞላበት ትርኢት ስመለከት
የአድዋ ጀግኖች መቃብር ከፍተው የተነሱ ይመስል ነበር።
ማለቴ ጥላሁን በድምፁ ብቻ ሳይሆን በቆይታው ጊዜን የማቆም ወይም ታሪክን የመቀስቀስ ኃይል እንደነበረው የመመልከት ዕድል አግኝቻለሁ ።
ጥላሁንን በዚያች ቅፅበት
በሕይወት እያለ ሐውልቱን አቁሞ አዳራሹ ውስጥ ታሪኩን ፅፎት ወጣ ።
በእርግጥ ሐውልት የማይናገርና የማይሰማ የድንጋይ ምስል ነው ጥላሁን ግን በሕይወት ያለ የሚተነፍስ የሚዘፍንና የሚራመድ የኢትዮጵያዊነት ሐውልት ነበር።
ዛሬም ቢሆን ስራዎቹ ያንን ግርማ ሞገስና ያንን ሐውልታዊ ፅናት እያስታወሱኝ እስከእለተ ሞቴ ድረስ ልረሳው አልችልም እንዲህ አይነት ድርጊት
ፍቅር ስሜት ብቻ አይደለም ራስን አሳልፎ መስጠት ነው በጥላሁን ገሰሰ የሀገር ፍቅር ዜማዎች ውስጥ ኢትዮጵያን ደጋግመን እናያታለን
አጥንቴም ይከስከስ ደሜም ይፍሰስላት የሚለው ቃል ዛሬም ድረስ ፍፁም ....ፍፁም መስዋዕትነት ነው።
ሀገሩን እንደ ሚወዳት እናት ወይም ሚስት አድርጎ ለሷ ክብር መሞትን እንደ ትልቅ ፀጋ መቁጠር ከፍ ያለ የፍቅር ደረጃ መግለጫ ነው።
ተመልካቹ በሙሉ ሳይቀመጥ ከሁለት ጊዜ በላይ ይደገም እያለ መጠየቁ ጥላሁን ድምፃዊ ብቻ ሳይሆን መሪ መሆኑን በአንድ ዜማ ሕዝብን የማስተሳሰር በአንድ ወኔ በጋራ የማቆም ተአምራዊ አቅሙን አረጋግጨበታለሁ ።
በዚያች ቅፅብት ቲያትር ቤቱ በጩሄትና በጭብጨባ ቀውጢ ሲሆን ጥላሁን ገሠሠ በድምፁ ብቻ የጠላትን ምሽግ የሚያፈርስ ጀግና መስሎ ነበር የሚታየው ።
ምንም እንኳን ዛሬ በሞት ቢለየንም ያ አስመራ ላይ የተመለከትኩት የሐገር ፍቅር ስሜት ሐውልት ሆኖ በልቤ ውስጥ ተቀርፆ ቆሟል።
ጥላሁን ገሰሰን ልዩ የሚደርገው ሌላው መገለጫው
ለፍቅር ሲዘፍን የፍቅር ሐውልት
ለሀገር ሲዘፍን የጀግንነት ሐውልት
ለሰው ልጅ ክብር ሲዘፍን የሰብአዊነት ሐውልት ነው!
ለዚህ ስኬት ደግሞ ከጥላሁን ድምፅ ጀርባ የነበሩት የወርቃማው ዘመን ታላላቅ የጥበብ ሰዎች ገጣሚያንና የዜማ አቀናባሪዎች ሚና ከፍተኛ እንደነበር ምስክሩ ታሪክና ሕዝቡ ነው።
ጥላሁን ገሰሰ ግጥምና ዜማን
ከነጄነራል አማኑኤል አብርሃም
ሻምበል አፈወርቅ ዮሐንስ
ነጋሽ ገብረማርያም
ተስፋዬ አበበ አየለ ማሞ ሳህሌ ደጋጎ ክፍሌ አቦቸር ከመሳሰሉት የክብር ዘበኛ እና የፖሊስ ኦርኬስትራዎች
ተቀብሎ ሲያንቆረቁረው ሙዚቃው ከድምፅ አልፎ የሚዳሰስ ሕያው መንፈስ የመሆን አቅም ነበረው።
ዛሬ ላይ ሆኜ ያንን ትርኢት ሳስታውሰው ጥላሁን ለኢትዮጵያ ሙዚቃና ለኢትዮጵያዊነት ያለው ትርጉም ምን ያህል ጥልቅ ስሜት እንደሆነ አሁን ድረስ እንደ ህልም ይታየኛል ።
ያኔ መድረክ ላይ ሲወጣ የነበረው ግርማ ሞገስና ድምፁ ሲስተጋባ የተሰማኝ ስሜት ዛሬም ድረስ ዘፈኑን ስሰማው "የጦር ፊታውራሪ" የነበረ ጀግና ያህል ትዝ ይለኛል !!
ጥላሁን በመድረክ ላይ የነበረውን የበላይነት እና የሕዝብን ስሜት የመምራት ብቃቱን በሚገባ የመግለፅ አቅም ነበረው ።
ጥላሁን ዝም ብሎ ድምፃዊ ሳይሆን በዜማው የታጠቀ የሀገር መከታ ወታደርም ሆኖ እንደነበረ ማሳያ ነው ።
ለዚህ ነው የጥላሁን ገሠሠ የሀገር ፍቅር ዜማዎች ከጊዜና ከቦታ በላይ የሆኑ ናቸው የሚባሉት ። ለዚህም ነው ዛሬ ላይ ሆነን ስንሰማው የዛሬ 130 ዓመት በፊት የተነገረውን የዳግማዊ ምኒልክን የክተት አዋጅ የሚመስለን ።
ይህ የሚያሳየው ደግሞ ጥላሁን የኢትዮጵያን ታሪክ ኩራትና ነፃነት በድምፅ ቀርጾ ትውልድ እንዲወርሰው ማድረጉን ነው።
ወዳጆቼ
ስለ ጥላሁን ገሠሠ የሀገር ፍቅር ስሜት ስንናገር እነዚህ ሶስት መሰረታዊ እውነታዎች ጎልተው ይታያኛል ።
የቁርጠኝነት ድምፁን ስናደዳምጠው ጥላሁን "አገሬን" ሲል ዝም ብሎ ስም አይጠራም ለሀገሩ የሚሞትላትና የሚሰዋላት መሆኑን በቃናው ውስጥ ይሰማል። አጥንቴም ይከስከስ የሚለው ስንኝ ለዚህ ትልቅ ማሳያ ነው።
ጥላሁን ለሀገር ሲዘፍን መላው ኢትዮጵያዊ በአንድነት ቆሞ ፊታውራሪዬ ብሎ እንዲከተለው ያደርጋል።
ይህ ደግሞ በታሪካችን ውስጥ የታየ ትልቅ የጥበብ ተጽዕኖ ነው።
ከ130 ዓመት በፊት የነበረውን የአድዋ ጀግንነት ዛሬ ላለው ትውልድ በስሜት አገናኝቶ ማቅረብ የሚችለው እንደ ጥላሁን ያለ "የታሪክ ድልድይና የታሪክ ባለአደራ" ሲኖር ብቻ ነው።
እንኳንስ ደስታየን የሰውነቴን ሠው
እንኳን ነፃነቴን ፀጋ ክብሬን ትቸው
በናት አገር ምድር በሚያውቀኝ በማውቀው ...
ስቃይ መከራዬን ከአንችው ዘንድ ያድርገው ። የሚለው
ጥላሁን ለኢትዮጵያ የነበረውን ፍቅር ከምንም በላይ የሚያሳይ ነው። ከባዕድ አገር ደስታ ይልቅ የሀገሩን መከራ የመረጠበት የሞቱ አጋጣሚ ደግሞ ለሀገሩ ያለውን ፍቅር በደሙ ያረጋገጠበት ታላቅ ክስተት ነው ።
ጥላሁን ከአሜሪካ ተነስቶ ለፋሲካ በዓል ወደ ሀገሩ መግባቱና በዚያው ዕለት ማረፉ፣ "በሀገሬ አፈር ልቀበር" የሚለውን ጥልቅ የኢትዮጵያዊያን ምኞት የፈጸመበት ነው ይህ ቀረኝ የማይል የሚያሰኘው እስከ መጨረሻው ትንፋሹ ድረስ ከሀገሩና ከሕዝቡ ጋር መቆየቱ ነው ።
ሲሞት መላው የአዲስ አበባ ሕዝብ በነቂስ ወጥቶ አስከሬኑን ሲሸኜው ጥላሁን ለሕዝቡ የሰጠውን ፍቅር ሕዝቡ በታላቅ ክብር የመለሰለት መሆኑን ቅድስት ስላሴ ቤተክርስቲያን ህያው ምስክር ናት ። ያ ለቅሶ የአንድ ድምፃዊ ስንብት ሳይሆን የኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጅና የልብ ትርታ ሽኝት ነበር።
ጥላሁን በሕይወቱና በሞቱ ሀገርን መውደድ ማለት ትርጉሙን እስከ ሞት ድረስ መታመንን አረጋግጦበታል።
ሰውን መውደድ ! አብሮ ማልቀስና መቆም ሙያን መውደድ እስከ መጨረሻዋ ትንፋሽ ድረስ መዘመር ለኢትዮጵያዊያን ከድምፃዊነት በላይ የአንድነት ምልክት መሆን ነው።
እኔ በዓይኔ ያየሁትን በልቤ የሰነድኩትን ይህንን ታሪክ ለሚቀጥለው ትውልድ ሊተላለፍ የሚገባው የፍቅርና የሀገር አምልኮ ትልቅ ትምህርት ይሆናል ብየ ሳዘጋጀው ጥላሁን ገሠሠ
ትንፋሼ ተቀርፆ ይቀመጥ ማልቀሻ ይህ ነው የሞትኩለት የኔ ማስታወሻ
ታሪኬ ነው ድምፄ በማለት ያንጎራጎረው ሙዚቃ ከፍቼ እያዳመጥኩ ነበር።
ይህ ስንኝ ጥላሁን ገሠሠ አስቀድሞ በድምፁ የህይወቱ ታሪክ የሞቱ ማስታወሻ እና የሀገሩ ውበት መገለጫ እንደሚሆን ተረድቶት የተጫወተው ነበር ማለት ይቻላል ። ጥላሁን በጥቁርና ነጭ ወረቀት ላይ የሰፈረ ኑዛዜ ሳይሆን የተውልን በህይወት ቆሞ በዜማ የተናዘዘው ድንቅ ስንብት ነበረ ።
እነዚህ ስንኞች የጥላሁንን የጥበብ ክብርና ትህትና ሲገለፅበት እያዳመጥኩት ነበር ይህን ታሪክ የፃፍኩት ።
ወዳጃቸ
የጥላሁን ገሠሠ ድምፅ ዝም ብሎ የአየር ንዝረት አይደለም፤ ማንነቱ፣ ታሪኩና ለሀገሩ የከፈለው መስዋዕትነት ነው። በጩኸት መኖሬን ማለቱ ለሀገርና ለፍቅር ሲል ድምፁን እስከ መጨረሻው የጥገታ ነጥብ ድረስ መጠቀሙንና ለዚህም መሞቱን ያሳያል።
ድምፄን ሰምቶ ያዝናል ለረገፈው አፅሜ ሲል
እጅግ ልብ ይነካል !
ጥላሁን በከፍታው ላይ ሆኖ እንኳ ያስቀየምኩት ቢኖር ብሎ ይቅርታን ይጠይቃል። የሞተውን አፅሙን ሳይሆን የቀረውን ድምፁን ሰምተው ሰዎች እንዲያዝኑለትና ይቅር እንዲሉት መመኘቱ የሰው ልጅነቱንይቅርታና ትህትናውን
ፍርጥ አድርጎ ያሳያል።
ጥላሁን ገሠሠ በድምፁና በህይወቱ የሰራው ትልቁ ስራ ፍቅርንና ኢትዮጵያዊነትን ማዳን ነበር። ጥላሁን ከቀላል ስሜትነት አልፎ ሕይወት መስዋዕትነትና የሀገር ፍቅር ጥግ መሆኑን በሚገባ አስገንዝቦናል።ጥበብ እንዴት የአንድን ሕዝብ ወኔና ማንነት እንደምትቀርፅ ጥላሁን ትልቅ ማሳያ ነው።
ፍቅር ተግባር ነው ፍቅር ዝም ብሎ የሚሰማን ስሜት ሳይሆን እንደ ጥላሁን ዜማዎች ራስን አሳልፎ እስከ መስጠት የሚደርስ ውሳኔ መሆኑን መረዳት ከባድ አይደለም ።
ጥላሁን ገሰሰ የሚዘፈነው ለጆሮ ብቻ ሳይሆን ለህሊና እና ለነፍስ ጭምር ይመስለኛል ።
ጥላሁን ዛሬ በሥጋ ቢለየንም ታሪኬ ነው ድምፄ ብሎ እንደተናዘዘው ሁሉ ዛሬም በየልባችን ውስጥ ንጉሥ ሆኖ ይኖራል።እሱ ለሀገር ብቻ ሳይሆን ለሰው ልጅ ስቃይ የሚራራ የህሊና ድምፅ ነበረው።
የሀገር ፍቅር ለአፈርና ለሰንደቅ ዓላማ የሚከፈል የአጥንትና የደም መስዋዕትነት ሲሆን ጥላሁን ገሠሠ በስጋ ቢለየንም ያ በሕይወት ያለ ሐውልት ግን በዜማዎቹ ውስጥ ሁሌም አዲስ ሆኖ ይኖራል።
ባጭሩ የጥላሁን መሞት ዝም ብሎ የአንድ ድምፃዊ ማለፍ ብቻ አልነበረም የአንድ ዘመን መቋጫ የአንድ ትልቅ ተስፋ መደብዘዝ እና በኢትዮጵያ ሰማይ ላይ የሚበራው የሙዚቃ ኮከብ ወድቆ ሲሰበር
ሰማይ ባዶ የሆነ ያህል ተሰምቶናል።
ጥላሁን ገሠሠ በደስታ ጊዜ አብሮን የሚጨፍር በጦርነት ጊዜ ፊታውራሪ ሆኖ የሚያዘምት በረሃብና በችግር ጊዜ ደግሞ አብሮን የሚላቀስ የሕዝብ ልብ ነበር ።
ጥላሁንን ከአቅም በላይ ያደረገው ይሄው ሁለንተናዊነቱ ነው። ለፍቅር ለሀገርና ለሰብአዊነት የነበረው ጽናት እሱ ሞቶም እንዲኖር አድርጎታል።
የጥላሁን ገሠሠ ዘፈኖች "ኢትዮጵያዊ ስነ-ሰብዕና" የሚባል የፍልስፍና ዘርፍ ቢኖር የዛ ዘርፍ ዋና መማሪያ መፅሐፍ ይሆኑ ነበር ።ብቻ
የጥላሁንገሰሰ ሕይወት ልክ እንደ አንድ የተቀደሰ መፅሐፍ በመሆኑ እራሡ ከፍቶ እራሱ ዘግቶት አልፏል ።
ለዚህ ታላቅ ድምፃዊ በተወለደበት ከተማ አዲስ አበባ ላይ ዘላለማዊ ምልክት ሆኖ እንዲቀመጥ ሐውልቱ ስለቆመለት ደስታዬ ወደር የለውም ።
ነፍስ ይማር !!
2 months ago
የኢትዮጵያ የርምጃ አትሌቶች ብራዚል ገቡ
#ethiopia | በደቡብ አሜሪካ ምድር የኢትዮጵያን ሰንደቅ ዓላማ ለማውለብለብ የጀግኖቹ ጉዞ ተጀምሯል!
በብራዚል በሚካሄደው የዓለም አትሌቲክስ የእርምጃ ውድድር ላይ የሚሳተፈው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ዛሬ ጠዋት ከቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ተነስቷል። ቡድኑ በፌዴሬሽኑ አመራሮች ደማቅ ሽኝት ተደርጎለታል።
ኢትዮጵያን የሚወክሉ ጀግኖች፦
አትሌት ምስጋና ዋቁማ
በፓሪስ ኦሎምፒክ ድንቅ ብቃት ያሳየውና በ20 ኪ.ሜ የሚወዳደረው።
አትሌት ህይወት አምባው
የአፍሪካ ወጣቶች ኦሎምፒክ የወርቅ ሜዳሊያ ባለቤት (በ10 ኪ.ሜ ሴቶች)።
አትሌት አቡዱሰላም አቡዱልወሀብ፦ በድሬደዋና በአዲስ አበባ የወጣቶች ሻምፒዮና አሸናፊ (በ10 ኪ.ሜ ወንዶች)።
ውድድሩ መጪው እሁድ በብራዚል የሚካሄድ ሲሆን፣ አትሌቶቻችን በድል ተመልሰው ሀገራዊ ኩራት እንደሚሆኑ ይጠበቃል።
ለመላው የልዑካን ቡድን መልካም ዕድል እንመኛለን!
#getu #ethiopianathletics #racewalking #worldathletics #brazil2026 #misganawakuma #teamethiopia #sportsnews #addisababa #አትሌቲክስ #እርምጃ #ኢትዮጵያ #ብራዚል #ጌጡተመስገን #getutemesgen
#ethiopia | በደቡብ አሜሪካ ምድር የኢትዮጵያን ሰንደቅ ዓላማ ለማውለብለብ የጀግኖቹ ጉዞ ተጀምሯል!
በብራዚል በሚካሄደው የዓለም አትሌቲክስ የእርምጃ ውድድር ላይ የሚሳተፈው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ዛሬ ጠዋት ከቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ተነስቷል። ቡድኑ በፌዴሬሽኑ አመራሮች ደማቅ ሽኝት ተደርጎለታል።
ኢትዮጵያን የሚወክሉ ጀግኖች፦
አትሌት ምስጋና ዋቁማ
በፓሪስ ኦሎምፒክ ድንቅ ብቃት ያሳየውና በ20 ኪ.ሜ የሚወዳደረው።
አትሌት ህይወት አምባው
የአፍሪካ ወጣቶች ኦሎምፒክ የወርቅ ሜዳሊያ ባለቤት (በ10 ኪ.ሜ ሴቶች)።
አትሌት አቡዱሰላም አቡዱልወሀብ፦ በድሬደዋና በአዲስ አበባ የወጣቶች ሻምፒዮና አሸናፊ (በ10 ኪ.ሜ ወንዶች)።
ውድድሩ መጪው እሁድ በብራዚል የሚካሄድ ሲሆን፣ አትሌቶቻችን በድል ተመልሰው ሀገራዊ ኩራት እንደሚሆኑ ይጠበቃል።
ለመላው የልዑካን ቡድን መልካም ዕድል እንመኛለን!
#getu #ethiopianathletics #racewalking #worldathletics #brazil2026 #misganawakuma #teamethiopia #sportsnews #addisababa #አትሌቲክስ #እርምጃ #ኢትዮጵያ #ብራዚል #ጌጡተመስገን #getutemesgen
2 months ago
♦️የኢትዮጵያ ሻምፒዮና ዳግም ውልደት
♦️አትሌቲክሱ ከማንዋል ወደ ዲጂታል መሸጋገሩን ያበሠረው ሻምፒዮና
♦️ልዩ ምስጋና የሚገባቸው ሁሉም የፌዴሬሽኑ ባለሙያዎች እና የአትሌቲክስ ዳኞች
👉1057 አትሌቶች ለሜዳልያ የተናነቁበት 55ኛው
ሻምፒዮና
#ethiopia | 36 ክለቦችና ተቋማት፣ 9 ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች፣621 ወንዶች፣ 436 ሴቶች በድምሩ 1057 አትሌቶች ለሜዳልያ የተናነቁበት 55ኛው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ተመልካቾችን ቁጭ ብድግ አድርጎ፣አዳዲስ ሪከርዶች ተሠባብረውበት፣ በተለይ በአጭር ርቀት የነገ የርቀቱ ንጉሶች ሊሆኑ ይችላሉ ተብለው የተገመቱ ተስፋዎች በብዛት ታይተውበት፣በዘመናዊ የውጤት መመዝገቢያ መሣሪያ(Time Tronics) ታጅቦና ዘምኖ በልዩ ድምቀት ተጠናቋል።
👉የሻምፒዮናው አጠቃላይ የአሸናፊነትን ዘውድ
የደፋው ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
በውድድሩ ለመሸናነፍና ለሜዳልያ ከሚደረገው ትንንቅ ባለፈ ለተተኪ አትሌቶች የውድድር እድል የመፍጠር፣የነገ ብቁና ውጤታማ አትሌቶችን ማፍራት ዋነኛ አላማው አድርጎ በተካሄደው ሻምፒዮና ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሻምፒዮናው አጠቃላይ የአሸናፊነትን ዘውድ ደፍቶ፣መቻል እና ኢትዮ ኤሌክትሪክ እንደየቅደም ተከተላቸው ሁለተኛና ሶስተኛ ደረጃን በመያዝ ተጠናቋል።
👉 ዳግም የተወለደው ዕድሜ ጠገቡ ሻምፒዮና
ከመክፈቻው እስከ መዝጊያው የነበረው ድባብ፣ሪከርዶች መሠባበራቸው፣በታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ ከ54 ዓመታት በኃላ በ Time Tronix መሳሪያ ታግዞና ዘምኖ የተጠናቀቀውን የኢትዮጵያ ሻምፒዮና ልብ ብሎ ለተመለከተው ዕድሜ ጠገቡ ሻምፒዮና ዳግም ተወልዷል ቢባል ቃሉ ግነት የለውም።
ከምንም በላይ ዘመኑን የዋጀ፣ከማንዋል ወደ ዲጂታል መሸጋገሩን ያበሠረ ታይም ትሮኒክስን በሻምፒዮናው መጠቀሙ ለአትሌቲክሱ ትንሳኤ፣ለአትሌቱ ደግሞ ከፍተኛ ደስታን ከማጎናፀፋቸው ሌላ በሁለቱም ፆታ በቦትስዋና ጋብሮኒ ለሚደረገው የአለም አትሌቲክስ ሪሌሚኒማ ለማሟላት ወደ ሌላ ሀገር የሚደረግ ስደትን፣የገንዘብ ብክነትንና ድካምን ያስወገደ ከመሆኑም በላይ በቀጣይ ፌዴሬሽኑ እያሠበ ላለው የብ/ቡድን ምስረታም አመላካችም ሆኖም ታይቷል።
👉የማይካደው የኮማንደር አትሌት ስለሺ ስህን የላቀ ሚና
ከ54 ዓመታት በኃላ የደመቀ ሻምፒዮና እንዲታይ የበርካቶች ጥረት እንዳለ መካድ ባይቻልም በተለይ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት የኮማንደር አትሌት ስለሺ ስህን ሚና ግን የላቀውን ቦታ ይይዛል።
ፕሬዝዳንቱ ኮማንደር አትሌት ስለሺ ስህን ሰባቱንም ቀን በአካል በመገኘት፣አስፈላጊውን መመሪያና አቅጣጫ በመስጠት፣በተለይ ከፍተኛ ወጪ ወጥቶበት ተጥሎ የነበረው ታይም ትሮኒክስ ከወደቀበት ተነስቶ አዋራው ተራግፎ ዳግም እንዲጠገን፣4 ባለሙያዎችን(2 ከቤልጅየም 1ከናይጄሪያ፣1 ዛምቢያ) በማስመጣት ለአገልግሎት እንዲውልና የውድድሩ ድምቀት እንዲሆን በሀገሪቱ የሚገኙ የስፖርት ሳይንስ ሙሁራንና ባለሙያዎችን በማሠባሠብ ብቁ የሠው ኃይል ለማፍራትና በሀገር አቅም ለመጠቀም ከውጪ በመጡ ባለሙያዎች ስልጠና በመስጠት በቀጣይ ውድድሮች በራሳችን ባለሙያዎች የሚመራበት ዕድል እንዲፈጠር ፕሬዝዳንቱ በቃላት የማይገለፅ ሚና መጫወታቸው ነው የተሠማው፤
ይሄ ብቻም አይደለም አራቱ የታይም ትሮኒክስ ባለሙያዎችም በቆይታቸው ተደስተው እንዲሄዱ፣በመንከባከብ፣የሽኝት እራት ፕሮግራም በማዘጋጀት፣በግላቸው ለውድድር የሚሆን ዶላር በማውጣትና ወጪዎቹን በመሸፈንና፣ከአለም አትሌቲክስ ጋር ፌዴሬሽኑ መልካም ግንኙነት እንዲኖረውም ከፍተኛ ስራ ሠርቷል፤ ስለዚህም ፕሬዝዳንት ኮማንደር አትሌት ስለሺ ስህን
ምስጋና የሚያንሠው ካልሆነ የሚበዛበት አይሆንም።
ውድድሩን በማስተባበር፣ቴክኖሎጂው እንዲተገበር በማድረግ በኩል የውድድሩ ዳይሬክተር አቶ ጊዜ አድነው እንዲሁም የአጭር ርቀት ውድድሮች ብ/ቡድን በመመስረት ጥሩ ስራ ሠርቷል፤የፅ/ቤት ኃላፊው አመንሲሳ ከበደ(ዶ/ር) በቦትስዋና የሚደረገው ውድድር ላይ ሚኒማ ለማሟላት ከዚህ በፊት ናይጄሪያ ድረስ ብዙ ወጪ ይወጣ የነበረውን የሚያስቀር አሠራር በመዘርጋታቸው የውድድሩን ከፍታ በመጨመራቸው እና ተስፋ ሰጪ መንገድ በማሳየታቸው ሁለቱ ምስጋና ይገባቸዋል ።
👉ሊመሠገኑ የሚገባቸው ባለሙያዎች
ከላይ ከተጠቀሱት በተጨማሪ ላለፉት 7 ቀናት የተካሄደው ሻምፒዮና እጅግ አድካሚና ፈታኝ ቢሆንም ፌዴሬሽኑ ውስጥ ያሉ የውድድር ባለሙያዎች፣አጠቃላይ የፌዴሬሽኑ ሙያተኞችና እና የአትሌቲክስ ዳኞችም ከጠዋቱ 12:00 ጀምሮ እስከ ማታ ድረስ በመስራት የውድድሩ ቅመሞች ሆነው በስኬት እንዲጠናቀቅ በማድረጋቸው ሁሉም የምስጋናው ፀበል ሊደርሳቸው ይገባል።
👉 ከ60 በላይ ጋዜጠኞች መታደማቸው ሌላኛው
የውድድሩ ሪከርድ
ቀደም ሲል ለአንድና ሁለት ሚዲያዎችና ጋዜጠኞች ብቻ በሩ ተከፍቶ ለሌሎች በመከርቸሙ ወደ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ደጃፍ ደርሠው የማያውቁትን ስመ-ጥር እና አንጋፋዎቹን ጨምሮ ከ60 በላይ ጋዜጠኞች ሻምፒዮናውን መታደማቸው ሌላኛው የፌዴሬሽኑ ስኬት ሲሆን የኮሚኒኬሽን(የህዝብ ግንኙነት)ከፍተኛ ባለሙያው መሀሪ ነጋሽ ሁሉም ጋዜጠኞች የቤታቸው ያህል እንዲሠማቸው፣አመለካከታቸው እንዲቀየር በማድረግ በኩል አኩሪ ስራ አከናውኗል ።
በተጨማሪም ወጣት መሀሪ ነጋሽ በፌዴሬሽኑ የማህበራዊ ትስስር ገፆች ፈጣን፣ቀልጣፋ ፣ተደራሽና ትኩስ መረጃ በማድረስ ቤተሠባዊነቱ ተጠናክሮ እንዲቀጥል የዘየደው ዘዴና የዘረጋው መስመር በመላው አለም ቀጥታ ስርጭት በማስተባበር እና ከውጭ የመጡት እንግዶችን አስፈላጊውን ድጋፍ በማድረግ በጎ ተግባር አከናውኗል ።
በተጨማሪም ውድድሩ ካለፋት ዓመታት በጣም በተሻለ የብራንዲንግ ስራ በመስራት ውድድሩ በውጪ አገር የሚካሄድ እስኪ መስል ድረስ ደረጃውን ከፍ በማድረግ የስፖርት ቤተሰቡን አስደምመዋል።
በዶክተር አያሌው የተመራው የህክምና ክፍልም ሳምንቱን ሙሉ ተቀናጅቶ በመስራትና ለተጎዱ አትሌቶች ተሎ በመድረስ ካለፈው ዓመት የተሻለ ስራ ሲሠራ ተስተውሏል።
በመዝጊያው መርሀ ግብር ላይ ሁሉም የፌዴሬሽኑ የስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባላት በሚባል ደረጃ ባልተለመደ መልኩ በአካል ተገኝተው መከታተላቸው እና እየተዘዋወሩ አትሌቶችን ማበረታታቸው የሚደነቅ አዲስ ጅምርም ሆኖ ታይቷል።
👉ማጠቃለያ:-ይታሠብበት
👉ሻምፒዮናው የደመቀ ቢሆንም እንከን
አልባ አልነበረም ማለት አይቻልም
በእርግጥ ውድድሩ ያማረና የደመቀ፣በተመልካችና በፉክክር የታጀበ፣በታይም ትሮኒክስ የታገዘ ሆኖ በድምቀት የተጠናቀቀ እንደሆነ ባይካድም እንከን አልባ አልነበረም ማለት ግን አይቻልም፤በዚህ በኩል በተለይ በታይም ትሮኒክስ አጠቃቀምና አተገባበር ዙሪያ ይስተዋሉ የነበሩ ክፍተቶች አትሌቶች ለውድድር ተዘጋጅተው ትራክ ላይ 20 እና 25 ደቂቃ የሚቆሙበት ክፍተት የሚጋነን ባይሆንም የውድድሩ ሠባራ ጎን ነበር፤
ይህ ትንሽ የሚመስል ስህተት በ One day meeting (ኮንትኔንታል ቱር)ላይ ክፍተት እንዳይፈጥር ከወዲሁ ስራ ሊሠራበትና ሊታሠብበት እንደሚገባ እየጠቆምን ባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ትራክ ከማዘጋጀት ጀምሮ ሶስት ሚኒስትሮች በመክፈቻው ዕለት በመገኘት ከቀን ጀምሮ እሰከማታ ከፌዴሬሽኑና ከውድድሩ ጎን በመቆም አትሌቶችን ማበረታታቸው ያስመሠግናቸዋል።
✍️✍️በጋዜጠኛ ይስሀቅ በላይ(ሀትሪክ ስፖርት ኦፊሺያል)
ፎቶ ክሬዲት: የኢ.አ.ፌ ይፋዊ የፌስቡክ ገጽ
♦️አትሌቲክሱ ከማንዋል ወደ ዲጂታል መሸጋገሩን ያበሠረው ሻምፒዮና
♦️ልዩ ምስጋና የሚገባቸው ሁሉም የፌዴሬሽኑ ባለሙያዎች እና የአትሌቲክስ ዳኞች
👉1057 አትሌቶች ለሜዳልያ የተናነቁበት 55ኛው
ሻምፒዮና
#ethiopia | 36 ክለቦችና ተቋማት፣ 9 ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች፣621 ወንዶች፣ 436 ሴቶች በድምሩ 1057 አትሌቶች ለሜዳልያ የተናነቁበት 55ኛው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ተመልካቾችን ቁጭ ብድግ አድርጎ፣አዳዲስ ሪከርዶች ተሠባብረውበት፣ በተለይ በአጭር ርቀት የነገ የርቀቱ ንጉሶች ሊሆኑ ይችላሉ ተብለው የተገመቱ ተስፋዎች በብዛት ታይተውበት፣በዘመናዊ የውጤት መመዝገቢያ መሣሪያ(Time Tronics) ታጅቦና ዘምኖ በልዩ ድምቀት ተጠናቋል።
👉የሻምፒዮናው አጠቃላይ የአሸናፊነትን ዘውድ
የደፋው ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
በውድድሩ ለመሸናነፍና ለሜዳልያ ከሚደረገው ትንንቅ ባለፈ ለተተኪ አትሌቶች የውድድር እድል የመፍጠር፣የነገ ብቁና ውጤታማ አትሌቶችን ማፍራት ዋነኛ አላማው አድርጎ በተካሄደው ሻምፒዮና ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሻምፒዮናው አጠቃላይ የአሸናፊነትን ዘውድ ደፍቶ፣መቻል እና ኢትዮ ኤሌክትሪክ እንደየቅደም ተከተላቸው ሁለተኛና ሶስተኛ ደረጃን በመያዝ ተጠናቋል።
👉 ዳግም የተወለደው ዕድሜ ጠገቡ ሻምፒዮና
ከመክፈቻው እስከ መዝጊያው የነበረው ድባብ፣ሪከርዶች መሠባበራቸው፣በታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ ከ54 ዓመታት በኃላ በ Time Tronix መሳሪያ ታግዞና ዘምኖ የተጠናቀቀውን የኢትዮጵያ ሻምፒዮና ልብ ብሎ ለተመለከተው ዕድሜ ጠገቡ ሻምፒዮና ዳግም ተወልዷል ቢባል ቃሉ ግነት የለውም።
ከምንም በላይ ዘመኑን የዋጀ፣ከማንዋል ወደ ዲጂታል መሸጋገሩን ያበሠረ ታይም ትሮኒክስን በሻምፒዮናው መጠቀሙ ለአትሌቲክሱ ትንሳኤ፣ለአትሌቱ ደግሞ ከፍተኛ ደስታን ከማጎናፀፋቸው ሌላ በሁለቱም ፆታ በቦትስዋና ጋብሮኒ ለሚደረገው የአለም አትሌቲክስ ሪሌሚኒማ ለማሟላት ወደ ሌላ ሀገር የሚደረግ ስደትን፣የገንዘብ ብክነትንና ድካምን ያስወገደ ከመሆኑም በላይ በቀጣይ ፌዴሬሽኑ እያሠበ ላለው የብ/ቡድን ምስረታም አመላካችም ሆኖም ታይቷል።
👉የማይካደው የኮማንደር አትሌት ስለሺ ስህን የላቀ ሚና
ከ54 ዓመታት በኃላ የደመቀ ሻምፒዮና እንዲታይ የበርካቶች ጥረት እንዳለ መካድ ባይቻልም በተለይ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት የኮማንደር አትሌት ስለሺ ስህን ሚና ግን የላቀውን ቦታ ይይዛል።
ፕሬዝዳንቱ ኮማንደር አትሌት ስለሺ ስህን ሰባቱንም ቀን በአካል በመገኘት፣አስፈላጊውን መመሪያና አቅጣጫ በመስጠት፣በተለይ ከፍተኛ ወጪ ወጥቶበት ተጥሎ የነበረው ታይም ትሮኒክስ ከወደቀበት ተነስቶ አዋራው ተራግፎ ዳግም እንዲጠገን፣4 ባለሙያዎችን(2 ከቤልጅየም 1ከናይጄሪያ፣1 ዛምቢያ) በማስመጣት ለአገልግሎት እንዲውልና የውድድሩ ድምቀት እንዲሆን በሀገሪቱ የሚገኙ የስፖርት ሳይንስ ሙሁራንና ባለሙያዎችን በማሠባሠብ ብቁ የሠው ኃይል ለማፍራትና በሀገር አቅም ለመጠቀም ከውጪ በመጡ ባለሙያዎች ስልጠና በመስጠት በቀጣይ ውድድሮች በራሳችን ባለሙያዎች የሚመራበት ዕድል እንዲፈጠር ፕሬዝዳንቱ በቃላት የማይገለፅ ሚና መጫወታቸው ነው የተሠማው፤
ይሄ ብቻም አይደለም አራቱ የታይም ትሮኒክስ ባለሙያዎችም በቆይታቸው ተደስተው እንዲሄዱ፣በመንከባከብ፣የሽኝት እራት ፕሮግራም በማዘጋጀት፣በግላቸው ለውድድር የሚሆን ዶላር በማውጣትና ወጪዎቹን በመሸፈንና፣ከአለም አትሌቲክስ ጋር ፌዴሬሽኑ መልካም ግንኙነት እንዲኖረውም ከፍተኛ ስራ ሠርቷል፤ ስለዚህም ፕሬዝዳንት ኮማንደር አትሌት ስለሺ ስህን
ምስጋና የሚያንሠው ካልሆነ የሚበዛበት አይሆንም።
ውድድሩን በማስተባበር፣ቴክኖሎጂው እንዲተገበር በማድረግ በኩል የውድድሩ ዳይሬክተር አቶ ጊዜ አድነው እንዲሁም የአጭር ርቀት ውድድሮች ብ/ቡድን በመመስረት ጥሩ ስራ ሠርቷል፤የፅ/ቤት ኃላፊው አመንሲሳ ከበደ(ዶ/ር) በቦትስዋና የሚደረገው ውድድር ላይ ሚኒማ ለማሟላት ከዚህ በፊት ናይጄሪያ ድረስ ብዙ ወጪ ይወጣ የነበረውን የሚያስቀር አሠራር በመዘርጋታቸው የውድድሩን ከፍታ በመጨመራቸው እና ተስፋ ሰጪ መንገድ በማሳየታቸው ሁለቱ ምስጋና ይገባቸዋል ።
👉ሊመሠገኑ የሚገባቸው ባለሙያዎች
ከላይ ከተጠቀሱት በተጨማሪ ላለፉት 7 ቀናት የተካሄደው ሻምፒዮና እጅግ አድካሚና ፈታኝ ቢሆንም ፌዴሬሽኑ ውስጥ ያሉ የውድድር ባለሙያዎች፣አጠቃላይ የፌዴሬሽኑ ሙያተኞችና እና የአትሌቲክስ ዳኞችም ከጠዋቱ 12:00 ጀምሮ እስከ ማታ ድረስ በመስራት የውድድሩ ቅመሞች ሆነው በስኬት እንዲጠናቀቅ በማድረጋቸው ሁሉም የምስጋናው ፀበል ሊደርሳቸው ይገባል።
👉 ከ60 በላይ ጋዜጠኞች መታደማቸው ሌላኛው
የውድድሩ ሪከርድ
ቀደም ሲል ለአንድና ሁለት ሚዲያዎችና ጋዜጠኞች ብቻ በሩ ተከፍቶ ለሌሎች በመከርቸሙ ወደ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ደጃፍ ደርሠው የማያውቁትን ስመ-ጥር እና አንጋፋዎቹን ጨምሮ ከ60 በላይ ጋዜጠኞች ሻምፒዮናውን መታደማቸው ሌላኛው የፌዴሬሽኑ ስኬት ሲሆን የኮሚኒኬሽን(የህዝብ ግንኙነት)ከፍተኛ ባለሙያው መሀሪ ነጋሽ ሁሉም ጋዜጠኞች የቤታቸው ያህል እንዲሠማቸው፣አመለካከታቸው እንዲቀየር በማድረግ በኩል አኩሪ ስራ አከናውኗል ።
በተጨማሪም ወጣት መሀሪ ነጋሽ በፌዴሬሽኑ የማህበራዊ ትስስር ገፆች ፈጣን፣ቀልጣፋ ፣ተደራሽና ትኩስ መረጃ በማድረስ ቤተሠባዊነቱ ተጠናክሮ እንዲቀጥል የዘየደው ዘዴና የዘረጋው መስመር በመላው አለም ቀጥታ ስርጭት በማስተባበር እና ከውጭ የመጡት እንግዶችን አስፈላጊውን ድጋፍ በማድረግ በጎ ተግባር አከናውኗል ።
በተጨማሪም ውድድሩ ካለፋት ዓመታት በጣም በተሻለ የብራንዲንግ ስራ በመስራት ውድድሩ በውጪ አገር የሚካሄድ እስኪ መስል ድረስ ደረጃውን ከፍ በማድረግ የስፖርት ቤተሰቡን አስደምመዋል።
በዶክተር አያሌው የተመራው የህክምና ክፍልም ሳምንቱን ሙሉ ተቀናጅቶ በመስራትና ለተጎዱ አትሌቶች ተሎ በመድረስ ካለፈው ዓመት የተሻለ ስራ ሲሠራ ተስተውሏል።
በመዝጊያው መርሀ ግብር ላይ ሁሉም የፌዴሬሽኑ የስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባላት በሚባል ደረጃ ባልተለመደ መልኩ በአካል ተገኝተው መከታተላቸው እና እየተዘዋወሩ አትሌቶችን ማበረታታቸው የሚደነቅ አዲስ ጅምርም ሆኖ ታይቷል።
👉ማጠቃለያ:-ይታሠብበት
👉ሻምፒዮናው የደመቀ ቢሆንም እንከን
አልባ አልነበረም ማለት አይቻልም
በእርግጥ ውድድሩ ያማረና የደመቀ፣በተመልካችና በፉክክር የታጀበ፣በታይም ትሮኒክስ የታገዘ ሆኖ በድምቀት የተጠናቀቀ እንደሆነ ባይካድም እንከን አልባ አልነበረም ማለት ግን አይቻልም፤በዚህ በኩል በተለይ በታይም ትሮኒክስ አጠቃቀምና አተገባበር ዙሪያ ይስተዋሉ የነበሩ ክፍተቶች አትሌቶች ለውድድር ተዘጋጅተው ትራክ ላይ 20 እና 25 ደቂቃ የሚቆሙበት ክፍተት የሚጋነን ባይሆንም የውድድሩ ሠባራ ጎን ነበር፤
ይህ ትንሽ የሚመስል ስህተት በ One day meeting (ኮንትኔንታል ቱር)ላይ ክፍተት እንዳይፈጥር ከወዲሁ ስራ ሊሠራበትና ሊታሠብበት እንደሚገባ እየጠቆምን ባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ትራክ ከማዘጋጀት ጀምሮ ሶስት ሚኒስትሮች በመክፈቻው ዕለት በመገኘት ከቀን ጀምሮ እሰከማታ ከፌዴሬሽኑና ከውድድሩ ጎን በመቆም አትሌቶችን ማበረታታቸው ያስመሠግናቸዋል።
✍️✍️በጋዜጠኛ ይስሀቅ በላይ(ሀትሪክ ስፖርት ኦፊሺያል)
ፎቶ ክሬዲት: የኢ.አ.ፌ ይፋዊ የፌስቡክ ገጽ
2 months ago
የጳውሎስ ረጋሳ ቀብር ሥነ ሥርዓት መረጃ
· ቀን፦ ነገ መጋቢት 16 ቀን 2018 ዓ.ም.
· ከሙምባይ አዲስ አበባ መድረሻ ‑ ከጠዋቱ 1:00 ሰዓት
· ከርክክብ በኋላ ጉዞ ወደ ቢሾፍቱ:- መኖርያ ቤት https://maps.app.goo.gl/ah...
· የቤተክርስትያን የሽኝት ፕሮግራም ከቀኑ 7፡00 እስከ 8፡30 (በደብረ ዘይት መካነ ኢየሱስ፣ ቢሾፍቱ ከተማ) https://maps.app.goo.gl/bA...
· ከቀኑ 9፡00 – 10፡00 የቀብር ስነሥርዓት፦ በቃጅማ የመካነ ኢየሱስ ቤተ ክርስትያን የቀብር ስፍራ፣ ቢሾፍቱ
https://maps.app.goo.gl/MR...
Odeeffannoo Sirna Awwaalchaa Phaawuloos Raggaasaa
· Guyyaa: Boru Bitootessa 16, bara 2018 A.L.I.
· Imala Mumbaayii irraa gara Finfinneetti gahu: ganama sa’aatii 1:00
· Erga simannaan xumuramee booda gara Bishooftuutti imala - Mana jireenyaa: https://maps.app.goo.gl/ah...
· Sagantaa gaggeessaan Waldaa: sa’aatii 7:00 hanga 8:30 (Waldaa Kiristaanaa Dabra Zait Makaana Yesus, Bishooftuuti) https://maps.app.goo.gl/bA...
· Sirna awwaalchaa: sa’aatii 9:00 – 10:00 (Bakka awwaalchaa Waldaa Kiristaanaa Makaana Yesus Qaajjimaa, Bishooftuuti) https://maps.app.goo.gl/MR...
Funeral Programme of Paulos Regassa
· Date፦ Tomorrow March 25, 2026
· Arrival in Addis Ababa from Mumbi – 7:00 AM
· Movement to Bishoftu after Reception at the Airport:- Destination: Residence https://maps.app.goo.gl/ah...
· Church Cerermony: From 13:00 to 14:30 (Debre Zeit Mekane Yesus Church, Bishoftu town) https://maps.app.goo.gl/bA...
· Funeral 15:00 to 16:00፦ At the Kajima Mekane Yesus Cemetery
https://maps.app.goo.gl/MR...
· ቀን፦ ነገ መጋቢት 16 ቀን 2018 ዓ.ም.
· ከሙምባይ አዲስ አበባ መድረሻ ‑ ከጠዋቱ 1:00 ሰዓት
· ከርክክብ በኋላ ጉዞ ወደ ቢሾፍቱ:- መኖርያ ቤት https://maps.app.goo.gl/ah...
· የቤተክርስትያን የሽኝት ፕሮግራም ከቀኑ 7፡00 እስከ 8፡30 (በደብረ ዘይት መካነ ኢየሱስ፣ ቢሾፍቱ ከተማ) https://maps.app.goo.gl/bA...
· ከቀኑ 9፡00 – 10፡00 የቀብር ስነሥርዓት፦ በቃጅማ የመካነ ኢየሱስ ቤተ ክርስትያን የቀብር ስፍራ፣ ቢሾፍቱ
https://maps.app.goo.gl/MR...
Odeeffannoo Sirna Awwaalchaa Phaawuloos Raggaasaa
· Guyyaa: Boru Bitootessa 16, bara 2018 A.L.I.
· Imala Mumbaayii irraa gara Finfinneetti gahu: ganama sa’aatii 1:00
· Erga simannaan xumuramee booda gara Bishooftuutti imala - Mana jireenyaa: https://maps.app.goo.gl/ah...
· Sagantaa gaggeessaan Waldaa: sa’aatii 7:00 hanga 8:30 (Waldaa Kiristaanaa Dabra Zait Makaana Yesus, Bishooftuuti) https://maps.app.goo.gl/bA...
· Sirna awwaalchaa: sa’aatii 9:00 – 10:00 (Bakka awwaalchaa Waldaa Kiristaanaa Makaana Yesus Qaajjimaa, Bishooftuuti) https://maps.app.goo.gl/MR...
Funeral Programme of Paulos Regassa
· Date፦ Tomorrow March 25, 2026
· Arrival in Addis Ababa from Mumbi – 7:00 AM
· Movement to Bishoftu after Reception at the Airport:- Destination: Residence https://maps.app.goo.gl/ah...
· Church Cerermony: From 13:00 to 14:30 (Debre Zeit Mekane Yesus Church, Bishoftu town) https://maps.app.goo.gl/bA...
· Funeral 15:00 to 16:00፦ At the Kajima Mekane Yesus Cemetery
https://maps.app.goo.gl/MR...
3 months ago
የመልካም ሰዎች መጉደል ለቤተ ክርስቲያን ነገ ያሳስባል"
- ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ
በሀገር ውስጥና በባህር ማዶ በነበረው የወንጌል አገልግሎቱ የሚታወቀው የወጣት መምህር ዘለዓለም ወንድሙ (ወልደ ሰማዕት) የቀብር ሥነ-ሥርዓት በአሁኑ ሰዓት በታላቁ ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል በታላቅ ድምቀትና ሐዘን እየተከናወነ ይገኛል።
ከመስቀል አደባባይ የጀመረውና በሺዎች የሚቆጠሩ ምእመናን የታደሙበት ይሄው የሽኝት መርሃ ግብር፣ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መሪዎችና ከፍተኛ የሃይማኖት አባቶች ታጅቦ ቀጥሏል።
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ፣ በመምህሩ ድንገተኛ ሕልፈት የተሰማቸውን ጥልቅ ሐዘን ገልጸዋል። በብፁዕ አቡነ ማቴዎስ አማካኝነት ለታዳሚው በንባብ በተሰማው የቅዱስነታቸው መልእክት ላይ የሚከተሉት ዋና ዋና ነጥቦች ተጠቅሰዋል፦
* መምህር ዘለዓለም በመንፈሳዊ ሕይወቱና በትጋቱ ለቤተ ክርስቲያን ትልቅ ተስፋ የነበረው፣ ወንጌልን ለማድረስ በገጠርም በከተማም የደከመ አባት መሆኑ ተገልጿል።
* "በምድር ያለው ማደሪያ ቤታችን ቢፈርስም በሰማይ የሰው እጅ ያልሠራው ዘለዓለማዊ ቤት እንዳለን እናውቃለን" (2ቆሮ. 5፡1) የሚለውን ቃለ እግዚአብሔር በመጥቀስ መጽናናትን አስተላልፈዋል።
* ቅዱስነታቸው በመልእክታቸው ውስጥ ሃይማኖትን ወይም ማንነትን መሠረት በማድረግ በቤተ ክርስቲያን አገልጋዮችና ምእመናን ላይ የሚደርሰው ጥቃት ልባቸውን በትካዜ ውስጥ እንደከተተው ሳይጠቅሱ አላለፉም።
መምህር ዘለዓለም ወንድሙ በሰሜን አሜሪካ ለአገልግሎት በሄደበት ወቅት ባጋጠመው ሕመም ከዚህ ዓለም በሥጋ መለየቱ ከፍተኛ ድንጋጤ የፈጠረ ቢሆንም፣ "ያለዋጋ የተቀበለውን የእግዚአብሔር ቃል ለምእመናን በማስተማር አደራውን በሚገባ ተወጥቷል" ሲሉ ቅዱስ ፓትርያርኩ ምስክርነታቸውን ሰጥተዋል።
በመጨረሻም፣ ሁሉን የሚችል አምላክ ለቤተሰቦቹና ለወዳጆቹ መጽናናትን እንዲሰጥ፣ ለቤተ ክርስቲያንም ተተኪ አገልጋዮችን እንዲያዘጋጅ አባታዊ ጸሎታቸውን አድርገዋል።
"ለአገልጋዩ ወልደ ሰማዕት ነፍስ እረፍተ መንግሥተ ሰማያትን እንመኛለን!"
#eotc
- ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ
በሀገር ውስጥና በባህር ማዶ በነበረው የወንጌል አገልግሎቱ የሚታወቀው የወጣት መምህር ዘለዓለም ወንድሙ (ወልደ ሰማዕት) የቀብር ሥነ-ሥርዓት በአሁኑ ሰዓት በታላቁ ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል በታላቅ ድምቀትና ሐዘን እየተከናወነ ይገኛል።
ከመስቀል አደባባይ የጀመረውና በሺዎች የሚቆጠሩ ምእመናን የታደሙበት ይሄው የሽኝት መርሃ ግብር፣ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መሪዎችና ከፍተኛ የሃይማኖት አባቶች ታጅቦ ቀጥሏል።
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ፣ በመምህሩ ድንገተኛ ሕልፈት የተሰማቸውን ጥልቅ ሐዘን ገልጸዋል። በብፁዕ አቡነ ማቴዎስ አማካኝነት ለታዳሚው በንባብ በተሰማው የቅዱስነታቸው መልእክት ላይ የሚከተሉት ዋና ዋና ነጥቦች ተጠቅሰዋል፦
* መምህር ዘለዓለም በመንፈሳዊ ሕይወቱና በትጋቱ ለቤተ ክርስቲያን ትልቅ ተስፋ የነበረው፣ ወንጌልን ለማድረስ በገጠርም በከተማም የደከመ አባት መሆኑ ተገልጿል።
* "በምድር ያለው ማደሪያ ቤታችን ቢፈርስም በሰማይ የሰው እጅ ያልሠራው ዘለዓለማዊ ቤት እንዳለን እናውቃለን" (2ቆሮ. 5፡1) የሚለውን ቃለ እግዚአብሔር በመጥቀስ መጽናናትን አስተላልፈዋል።
* ቅዱስነታቸው በመልእክታቸው ውስጥ ሃይማኖትን ወይም ማንነትን መሠረት በማድረግ በቤተ ክርስቲያን አገልጋዮችና ምእመናን ላይ የሚደርሰው ጥቃት ልባቸውን በትካዜ ውስጥ እንደከተተው ሳይጠቅሱ አላለፉም።
መምህር ዘለዓለም ወንድሙ በሰሜን አሜሪካ ለአገልግሎት በሄደበት ወቅት ባጋጠመው ሕመም ከዚህ ዓለም በሥጋ መለየቱ ከፍተኛ ድንጋጤ የፈጠረ ቢሆንም፣ "ያለዋጋ የተቀበለውን የእግዚአብሔር ቃል ለምእመናን በማስተማር አደራውን በሚገባ ተወጥቷል" ሲሉ ቅዱስ ፓትርያርኩ ምስክርነታቸውን ሰጥተዋል።
በመጨረሻም፣ ሁሉን የሚችል አምላክ ለቤተሰቦቹና ለወዳጆቹ መጽናናትን እንዲሰጥ፣ ለቤተ ክርስቲያንም ተተኪ አገልጋዮችን እንዲያዘጋጅ አባታዊ ጸሎታቸውን አድርገዋል።
"ለአገልጋዩ ወልደ ሰማዕት ነፍስ እረፍተ መንግሥተ ሰማያትን እንመኛለን!"
#eotc
3 months ago
የመልካም ሰዎች መጉደል ለቤተ ክርስቲያን ነገ ያሳስባል"
- ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ
#ethiopia | በሀገር ውስጥና በባህር ማዶ በነበረው የወንጌል አገልግሎቱ የሚታወቀው የወጣት መምህር ዘለዓለም ወንድሙ (ወልደ ሰማዕት) የቀብር ሥነ-ሥርዓት በአሁኑ ሰዓት በታላቁ ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል በታላቅ ድምቀትና ሐዘን እየተከናወነ ይገኛል።
ከመስቀል አደባባይ የጀመረውና በሺዎች የሚቆጠሩ ምእመናን የታደሙበት ይሄው የሽኝት መርሃ ግብር፣ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መሪዎችና ከፍተኛ የሃይማኖት አባቶች ታጅቦ ቀጥሏል።
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ፣ በመምህሩ ድንገተኛ ሕልፈት የተሰማቸውን ጥልቅ ሐዘን ገልጸዋል። በብፁዕ አቡነ ማቴዎስ አማካኝነት ለታዳሚው በንባብ በተሰማው የቅዱስነታቸው መልእክት ላይ የሚከተሉት ዋና ዋና ነጥቦች ተጠቅሰዋል፦
* መምህር ዘለዓለም በመንፈሳዊ ሕይወቱና በትጋቱ ለቤተ ክርስቲያን ትልቅ ተስፋ የነበረው፣ ወንጌልን ለማድረስ በገጠርም በከተማም የደከመ አባት መሆኑ ተገልጿል።
* "በምድር ያለው ማደሪያ ቤታችን ቢፈርስም በሰማይ የሰው እጅ ያልሠራው ዘለዓለማዊ ቤት እንዳለን እናውቃለን" (2ቆሮ. 5፡1) የሚለውን ቃለ እግዚአብሔር በመጥቀስ መጽናናትን አስተላልፈዋል።
* ቅዱስነታቸው በመልእክታቸው ውስጥ ሃይማኖትን ወይም ማንነትን መሠረት በማድረግ በቤተ ክርስቲያን አገልጋዮችና ምእመናን ላይ የሚደርሰው ጥቃት ልባቸውን በትካዜ ውስጥ እንደከተተው ሳይጠቅሱ አላለፉም።
መምህር ዘለዓለም ወንድሙ በሰሜን አሜሪካ ለአገልግሎት በሄደበት ወቅት ባጋጠመው ሕመም ከዚህ ዓለም በሥጋ መለየቱ ከፍተኛ ድንጋጤ የፈጠረ ቢሆንም፣ "ያለዋጋ የተቀበለውን የእግዚአብሔር ቃል ለምእመናን በማስተማር አደራውን በሚገባ ተወጥቷል" ሲሉ ቅዱስ ፓትርያርኩ ምስክርነታቸውን ሰጥተዋል።
በመጨረሻም፣ ሁሉን የሚችል አምላክ ለቤተሰቦቹና ለወዳጆቹ መጽናናትን እንዲሰጥ፣ ለቤተ ክርስቲያንም ተተኪ አገልጋዮችን እንዲያዘጋጅ አባታዊ ጸሎታቸውን አድርገዋል።
"ለአገልጋዩ ወልደ ሰማዕት ነፍስ እረፍተ መንግሥተ ሰማያትን እንመኛለን!"
#eotc
- ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ
#ethiopia | በሀገር ውስጥና በባህር ማዶ በነበረው የወንጌል አገልግሎቱ የሚታወቀው የወጣት መምህር ዘለዓለም ወንድሙ (ወልደ ሰማዕት) የቀብር ሥነ-ሥርዓት በአሁኑ ሰዓት በታላቁ ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል በታላቅ ድምቀትና ሐዘን እየተከናወነ ይገኛል።
ከመስቀል አደባባይ የጀመረውና በሺዎች የሚቆጠሩ ምእመናን የታደሙበት ይሄው የሽኝት መርሃ ግብር፣ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መሪዎችና ከፍተኛ የሃይማኖት አባቶች ታጅቦ ቀጥሏል።
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ፣ በመምህሩ ድንገተኛ ሕልፈት የተሰማቸውን ጥልቅ ሐዘን ገልጸዋል። በብፁዕ አቡነ ማቴዎስ አማካኝነት ለታዳሚው በንባብ በተሰማው የቅዱስነታቸው መልእክት ላይ የሚከተሉት ዋና ዋና ነጥቦች ተጠቅሰዋል፦
* መምህር ዘለዓለም በመንፈሳዊ ሕይወቱና በትጋቱ ለቤተ ክርስቲያን ትልቅ ተስፋ የነበረው፣ ወንጌልን ለማድረስ በገጠርም በከተማም የደከመ አባት መሆኑ ተገልጿል።
* "በምድር ያለው ማደሪያ ቤታችን ቢፈርስም በሰማይ የሰው እጅ ያልሠራው ዘለዓለማዊ ቤት እንዳለን እናውቃለን" (2ቆሮ. 5፡1) የሚለውን ቃለ እግዚአብሔር በመጥቀስ መጽናናትን አስተላልፈዋል።
* ቅዱስነታቸው በመልእክታቸው ውስጥ ሃይማኖትን ወይም ማንነትን መሠረት በማድረግ በቤተ ክርስቲያን አገልጋዮችና ምእመናን ላይ የሚደርሰው ጥቃት ልባቸውን በትካዜ ውስጥ እንደከተተው ሳይጠቅሱ አላለፉም።
መምህር ዘለዓለም ወንድሙ በሰሜን አሜሪካ ለአገልግሎት በሄደበት ወቅት ባጋጠመው ሕመም ከዚህ ዓለም በሥጋ መለየቱ ከፍተኛ ድንጋጤ የፈጠረ ቢሆንም፣ "ያለዋጋ የተቀበለውን የእግዚአብሔር ቃል ለምእመናን በማስተማር አደራውን በሚገባ ተወጥቷል" ሲሉ ቅዱስ ፓትርያርኩ ምስክርነታቸውን ሰጥተዋል።
በመጨረሻም፣ ሁሉን የሚችል አምላክ ለቤተሰቦቹና ለወዳጆቹ መጽናናትን እንዲሰጥ፣ ለቤተ ክርስቲያንም ተተኪ አገልጋዮችን እንዲያዘጋጅ አባታዊ ጸሎታቸውን አድርገዋል።
"ለአገልጋዩ ወልደ ሰማዕት ነፍስ እረፍተ መንግሥተ ሰማያትን እንመኛለን!"
#eotc
3 months ago
🙏 "የእግዚአብሔርን ሐሳብ ካገለገለ በኋላ አንቀላፋ!"
(የሐዋ. 13:36)
#ethiopia | ታላቁ የጥበብ መምህር፣ የብዙዎች አባትና መሪ የነበረው መምህር ዘላለም ወንድሙ፣ የክብር ሽኝቱ በመቀጠል ክቡር አስከሬኑ አሁን መስቀል አደባባይ ደርሷል።
ይህ ታላቅ የጥበብ ሰው በሕይወት ዘመኑ የጥበብን ዘር በመዝራት፣ ባለሙያዎችን በማፍራትና ለእውነት በመቆም የፈጣሪን ሐሳብ ሲያገለግል ቆይቶ፣ እነሆ ዛሬ በክብር ወደ መጨረሻው ማረፊያው እየተሸኘ ይገኛል።
የጸሎትና የሐዘን መግለጫ
"ኦ እግዚኦ አዕርፍ ነፍሰ እኁነ ወልደ ሰማዕት ሀገረ ሕይወት መንግሥተ ሰማያትን ያወርስልን፤ በአባቶቻችን በአብርሃም በይስሐቅ በያዕቆብ ዕቅፍ ያኑርልን!"
መምህር ዘላለም ለኢትዮጵያ ቴአትርና ፊልም ጥበብ ያበረከተው አስተዋጽኦ በትውልድ ቅብብሎሽ ውስጥ ለዘላለም ሲታወስ ይኖራል። ሞት ሥጋን እንጂ ሥራንና መልካም ስምን አይቀብርምና መምህር ዘላለም በሥራዎቹ ሁሌም ሕያው ነው።
የሽኝቱ ሁኔታ
በአሁኑ ሰዓት በመስቀል አደባባይ በሚደረገው የክብር ስንብት ላይ፦
የቤተክርስቲያን አባቶች፣
የመንግሥት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች፣
አንጋፋና ወጣት የጥበብ ባለሙያዎች፣
እንዲሁም በሺዎች የሚቆጠሩ አድናቂዎቹና ወዳጆቹ በመገኘት የመጨረሻ ክብራቸውን እየገለጹ ይገኛሉ።
ፈጣሪ ለቤተሰቦቹ፣ ለወዳጆቹና ለመላው የጥበብ ቤተሰብ መጽናናትን ይስጥልን።
ነፍስ ይማር!
#መምህርዘላለምወንድሙ #ዘላለምወንድሙ #የክብርሽኝት #መስቀልአደባባይ #ኢትዮጵያ #ጥበብ #zelalemwondimu #ethiopia #artfamily #getu #temesgen #getutemesgen #ጌጡ #ተመስገን #ጌጡተመስገን
(የሐዋ. 13:36)
#ethiopia | ታላቁ የጥበብ መምህር፣ የብዙዎች አባትና መሪ የነበረው መምህር ዘላለም ወንድሙ፣ የክብር ሽኝቱ በመቀጠል ክቡር አስከሬኑ አሁን መስቀል አደባባይ ደርሷል።
ይህ ታላቅ የጥበብ ሰው በሕይወት ዘመኑ የጥበብን ዘር በመዝራት፣ ባለሙያዎችን በማፍራትና ለእውነት በመቆም የፈጣሪን ሐሳብ ሲያገለግል ቆይቶ፣ እነሆ ዛሬ በክብር ወደ መጨረሻው ማረፊያው እየተሸኘ ይገኛል።
የጸሎትና የሐዘን መግለጫ
"ኦ እግዚኦ አዕርፍ ነፍሰ እኁነ ወልደ ሰማዕት ሀገረ ሕይወት መንግሥተ ሰማያትን ያወርስልን፤ በአባቶቻችን በአብርሃም በይስሐቅ በያዕቆብ ዕቅፍ ያኑርልን!"
መምህር ዘላለም ለኢትዮጵያ ቴአትርና ፊልም ጥበብ ያበረከተው አስተዋጽኦ በትውልድ ቅብብሎሽ ውስጥ ለዘላለም ሲታወስ ይኖራል። ሞት ሥጋን እንጂ ሥራንና መልካም ስምን አይቀብርምና መምህር ዘላለም በሥራዎቹ ሁሌም ሕያው ነው።
የሽኝቱ ሁኔታ
በአሁኑ ሰዓት በመስቀል አደባባይ በሚደረገው የክብር ስንብት ላይ፦
የቤተክርስቲያን አባቶች፣
የመንግሥት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች፣
አንጋፋና ወጣት የጥበብ ባለሙያዎች፣
እንዲሁም በሺዎች የሚቆጠሩ አድናቂዎቹና ወዳጆቹ በመገኘት የመጨረሻ ክብራቸውን እየገለጹ ይገኛሉ።
ፈጣሪ ለቤተሰቦቹ፣ ለወዳጆቹና ለመላው የጥበብ ቤተሰብ መጽናናትን ይስጥልን።
ነፍስ ይማር!
#መምህርዘላለምወንድሙ #ዘላለምወንድሙ #የክብርሽኝት #መስቀልአደባባይ #ኢትዮጵያ #ጥበብ #zelalemwondimu #ethiopia #artfamily #getu #temesgen #getutemesgen #ጌጡ #ተመስገን #ጌጡተመስገን
Sponsored by
Surafel
3 months ago
የሽኝት ዜማ
ትንሣኤ አለን !!
#ethiopia | ለመምህር ዘላለም ወንድሙ የሽኝት የዝማሬ ዜማ ተዘጋጀ።
በዘምሪት የትምወርቅ ሙላት አስተባባሪነት በዜማ ሰማያት የተዘጋጀው ዝማሬ በሠላሣ ስድስቱ እህትማማቾች ዘማሪያት የተዘመረ ሲሆን ለብዙዎች መጽናናት እንዲሆን በማሰብ በፍቅርና በእንባ የቀረበ እንደሆነ ተገልጿል።
ይሄ የሚሞተው የማይሞት ይለብሳል
አዲስ አካል ሆኖ በህይወት ይነሳል
ነጩን ልብስ ለብሰን ከመላእክት ጋራ
እንገናኛለን በዝማሬ ሥራ
ትንሣኤ አለን ...እንነሳለን ...
በአዲስ አካል እንገለጣለን
ትንሣኤ አለን !!
#ethiopia | ለመምህር ዘላለም ወንድሙ የሽኝት የዝማሬ ዜማ ተዘጋጀ።
በዘምሪት የትምወርቅ ሙላት አስተባባሪነት በዜማ ሰማያት የተዘጋጀው ዝማሬ በሠላሣ ስድስቱ እህትማማቾች ዘማሪያት የተዘመረ ሲሆን ለብዙዎች መጽናናት እንዲሆን በማሰብ በፍቅርና በእንባ የቀረበ እንደሆነ ተገልጿል።
ይሄ የሚሞተው የማይሞት ይለብሳል
አዲስ አካል ሆኖ በህይወት ይነሳል
ነጩን ልብስ ለብሰን ከመላእክት ጋራ
እንገናኛለን በዝማሬ ሥራ
ትንሣኤ አለን ...እንነሳለን ...
በአዲስ አካል እንገለጣለን
3 months ago
🕯️ የመምህር ዘለዓለም ወንድሙ (ወልደ ሰማዕት) የሽኝት መርሐ-ግብር
በሰሜን አሜሪካ ዋሽንግተን ዲሲ ርእሰ አድባራት ደብረ ሰላም ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን የሚከናወነው የታዋቂው መምህር ዘለዓለም ወንድሙ የአስክሬን ሽኝት መርሐ-ግብር ዝርዝር ይፋ ሆኗል። መርሐ-ግብሩ ከዛሬ እሑድ ጀምሮ እስከ ማክሰኞ ድረስ በተለያዩ ሃይማኖታዊ ሥነ-ሥርዓቶች ይከናወናል።
የጊዜ ሰሌዳ (ዋሽንግተን ዲሲ)
፩. እሑድ የካቲት 29 ቀን 2018 ዓ.ም (March 8, 2026)
ጸሎተ ፍትሐት፦ በሀገረ ስብከቱ በሚገኙ አብያተ ክርስቲያናት ሁሉ ይከናወናል።
የሀዘን መግለጫ፦
ከቅዳሴ በኋላ በደብረ ሰላም ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን የላይኛው መኪና ማቆሚያ ላይ አገልጋዮችና ምእመናን ተሰብስበው ሀዘናቸውን ይገልጻሉ።
፪. ሰኞ የካቲት 30 ቀን 2018 ዓ.ም (March 9, 2026)
ለቅሶ መድረሻ፦ ከቀኑ 6:00 (12pm) - 10:00 (4pm) ሰዓት በላይኛው ትራቨለር ለቅሶ መድረስ ለሚፈልጉ ክፍት ይሆናል።
የሠርክ ጸሎት፦ ከቀኑ 10:30 (4:30pm) - 1:30 (7:30pm) በትምህርተ ወንጌልና በውዳሴ ማርያም መዝከር ይከናወናል።
ወደ ቤተክርስቲያን መግባት፦ ከምሽቱ 1:00 (7pm) ክቡር አስከሬኑ ወደ ቤተክርስቲያን ይገባል።
የሌሊት ማህሌት፦ ከሌሊቱ 7:00 (1am) ጀምሮ አገልጋዮችና ምእመናን ሰዓታት ቆመው ያድራሉ።
፫. ማክሰኞ መጋቢት 1 ቀን 2018 ዓ.ም (March 10, 2026)
ጸሎተ ፍትሐት፦ ከጠዋቱ 3:00 (9am) - 6:00 (12pm) ይከናወናል።
ምስክርነት፦ ከቀኑ 6:00 (12pm) ጀምሮ የሕይወት ታሪክና የወዳጅ ዘመድ ምስክርነት ይሰጣል።
ትምህርተ ወንጌልና ቡራኬ፦ በፓትርያርኩ አጭር ትምህርተ ወንጌል እንዲሁም በብጹዕ አቡነ ፋኑኤል ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ ይሰጣል።
ሽኝት፦ ከሥነ-ሥርዓቱ በኋላ ክቡር አስከሬኑ ወደ ትውልድ ሀገሩ ኢትዮጵያ ሽኝት ይደረግለታል።
⚠️ ጠቃሚ ማሳሰቢያዎች
የአለባበስ ሥርዓት፦
በፍትሐቱና በሽኝቱ ላይ የሚገኙ አገልጋዮችና ምእመናን በሙሉ ነጭ ልብስ ለብሰው እንዲገኙ በአክብሮት ተጠይቀዋል።
አድራሻ፦
1350 Buchanan St. NW, Washington, D.C 20011
"ኦ እግዚኦ አእርፍ ለነፍሰ ገብረከ ወልደ ሰማዕት!"
(አቤቱ የባሪያህን የወልደ ሰማዕትን ነፍስ አሳርፍ!)
የመምህራችንን ነፍስ ከቅዱሳን ጋር ይደምርልን፤ ለቤተሰቦቹና ለወዳጆቹም መፅናናትን ይስጥልን።
#መምህርዘለዓለምወንድሙ #ወልደሰማዕት #ኦርቶዶክስ #ኢትዮጵያ #ዋሽንግተንዲሲ #ሽኝት #getu #temesgen #getutemesgen #ጌጡ #ተመስገን #ጌጡተመስገን
በሰሜን አሜሪካ ዋሽንግተን ዲሲ ርእሰ አድባራት ደብረ ሰላም ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን የሚከናወነው የታዋቂው መምህር ዘለዓለም ወንድሙ የአስክሬን ሽኝት መርሐ-ግብር ዝርዝር ይፋ ሆኗል። መርሐ-ግብሩ ከዛሬ እሑድ ጀምሮ እስከ ማክሰኞ ድረስ በተለያዩ ሃይማኖታዊ ሥነ-ሥርዓቶች ይከናወናል።
የጊዜ ሰሌዳ (ዋሽንግተን ዲሲ)
፩. እሑድ የካቲት 29 ቀን 2018 ዓ.ም (March 8, 2026)
ጸሎተ ፍትሐት፦ በሀገረ ስብከቱ በሚገኙ አብያተ ክርስቲያናት ሁሉ ይከናወናል።
የሀዘን መግለጫ፦
ከቅዳሴ በኋላ በደብረ ሰላም ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን የላይኛው መኪና ማቆሚያ ላይ አገልጋዮችና ምእመናን ተሰብስበው ሀዘናቸውን ይገልጻሉ።
፪. ሰኞ የካቲት 30 ቀን 2018 ዓ.ም (March 9, 2026)
ለቅሶ መድረሻ፦ ከቀኑ 6:00 (12pm) - 10:00 (4pm) ሰዓት በላይኛው ትራቨለር ለቅሶ መድረስ ለሚፈልጉ ክፍት ይሆናል።
የሠርክ ጸሎት፦ ከቀኑ 10:30 (4:30pm) - 1:30 (7:30pm) በትምህርተ ወንጌልና በውዳሴ ማርያም መዝከር ይከናወናል።
ወደ ቤተክርስቲያን መግባት፦ ከምሽቱ 1:00 (7pm) ክቡር አስከሬኑ ወደ ቤተክርስቲያን ይገባል።
የሌሊት ማህሌት፦ ከሌሊቱ 7:00 (1am) ጀምሮ አገልጋዮችና ምእመናን ሰዓታት ቆመው ያድራሉ።
፫. ማክሰኞ መጋቢት 1 ቀን 2018 ዓ.ም (March 10, 2026)
ጸሎተ ፍትሐት፦ ከጠዋቱ 3:00 (9am) - 6:00 (12pm) ይከናወናል።
ምስክርነት፦ ከቀኑ 6:00 (12pm) ጀምሮ የሕይወት ታሪክና የወዳጅ ዘመድ ምስክርነት ይሰጣል።
ትምህርተ ወንጌልና ቡራኬ፦ በፓትርያርኩ አጭር ትምህርተ ወንጌል እንዲሁም በብጹዕ አቡነ ፋኑኤል ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ ይሰጣል።
ሽኝት፦ ከሥነ-ሥርዓቱ በኋላ ክቡር አስከሬኑ ወደ ትውልድ ሀገሩ ኢትዮጵያ ሽኝት ይደረግለታል።
⚠️ ጠቃሚ ማሳሰቢያዎች
የአለባበስ ሥርዓት፦
በፍትሐቱና በሽኝቱ ላይ የሚገኙ አገልጋዮችና ምእመናን በሙሉ ነጭ ልብስ ለብሰው እንዲገኙ በአክብሮት ተጠይቀዋል።
አድራሻ፦
1350 Buchanan St. NW, Washington, D.C 20011
"ኦ እግዚኦ አእርፍ ለነፍሰ ገብረከ ወልደ ሰማዕት!"
(አቤቱ የባሪያህን የወልደ ሰማዕትን ነፍስ አሳርፍ!)
የመምህራችንን ነፍስ ከቅዱሳን ጋር ይደምርልን፤ ለቤተሰቦቹና ለወዳጆቹም መፅናናትን ይስጥልን።
#መምህርዘለዓለምወንድሙ #ወልደሰማዕት #ኦርቶዶክስ #ኢትዮጵያ #ዋሽንግተንዲሲ #ሽኝት #getu #temesgen #getutemesgen #ጌጡ #ተመስገን #ጌጡተመስገን
3 months ago
የመምህር ዘላለም ወንድሙ (ወለደ ሰማዕት) ክቡር አስከሬን ሽኝትን በተመለከተ የተዘጋጀ መርሐ ግብር
"እንግዲህ ሂዱና አሕዛብን ሁሉ በአብ በወልድና በመንፈስ ቅዱስ ስም እያጠመቃችኋቸው ያዘዝኋችሁንም ሁሉ እንዲጠብቁ እያስተማራችኋቸው ደቀ መዛሙርት አድርጓቸው።" ማቴ 28፡19
“የአገልጋይን ሰው ሞት ቸል አትበል ምርር ብለህ አልቅስለት አጽናንተው አዝንለት እንደ ሀገሩ ልማድ አልቅስለት ስለ ሀገሩ ልማድ አንድ ቀን ሁለት ቀን አልቅስለት የብስጭት ሀይል የሚያደክም ስለሆነ ስለ ብስጭት ሀዘን እንዳይገባህ ከዚህ በኋላ ልቅሶህን ተው።” መጽሐፈ ሲራክ 38 16-18
መርሐ ግብር:-
* እሁድ የካቲት 29 ቀን 2018 ዓ.ም (March 8, 2026) በዋሽንግተን ዲሲ እና አካባቢው ሀገረ ስብከት ባሉ አብያተ ክርስቲያናት ጸሎተ ፍትሐት ይደረጋል።
1. እሁድ ከቅዳሴ በኋላ በርእሰ አድባራት ደብረ ሰላም ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን ቅጽረ ግቢ በላይኛው መኪና ማቆሚያ የአካባቢው አድባራት እና ገዳማት አገልጋዮች እና ሕዝበ ክርስቲያኑ ተሰብስበው ሀዘናቸውን ይገልጻሉ።
2. ሰኞ የካቲት 30 ቀን 2018 ዓ.ም (March 9, 2026) ከቀኑ 12pm - 4pm ሰዓት ጀምሮ በላይኛው ትራቨለር ለቅሶ መድረስ ለሚፈልጉ ሁሉ ቦታው ክፍት ይሆናል።
4. ሰኞ ከቀኑ 4:30pm - 7:30pm የአካባቢው አድባራት እና ገዳማት አገልጋዮች እና ሕዝበ ክርስቲያኑ ተሰብስበው በሠርክ ጸሎት እና በትምህርተ ወንጌል፣ በውዳሴ ማርያም ሥነ ሥርዓት ሲዘክሩ ያመሻሉ።
5. ሰኞ ከምሽቱ 7 ሰዓት ክቡር አስከሬኑ ወደ ቤተ ክርስቲያን ይገባል።
6. ከሌሊቱ 1am የአካባቢው አድባራት እና ገዳማት አገልጋዮች እና ሕዝበ ክርስቲያኑ ተሰብስበው በሰዓታት ቆመው ያድራሉ።
7. ማክሰኞ ከጠዋቱ 9am - 12pm የአካባቢው አድባራት እና ገዳማት አገልጋዮች እና ሕዝበ ክርስቲያኑ ተሰብስበው ጸሎተ ፍትሐት ይደረጋል።
8. ማክሰኞ 12pm የመምህር ዘላለም ወንድሙ የሕይወት ታሪክ እና የወዳጅ ዘመድ ምስክርነት ይሰጣል።
9. ማክሰኞ በፓትርያርኩ አጭር ትምህርተ ወንጌል ይሰጣል።
10. ማክሰኞ በሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ በብጹዕ አቡነ ፋኑኤል ቃለ ምዕዳን እና ቡራኬ ተሰጥቶ ክቡር አስከሬኑ ወደ ትውልድ ሀገሩ ኢትዮጵያ ሽኝት ከተደረገ በኋላ ለመታሰቢያ የተዘጋጀው ጸበል ጻዲቅ ተቀምጦ የመርሐ ግብሩ ፍጻሜ ይሆናል። የመምህራችን የወለደ ሰማዕትን ነፍስ ከቅዱሳን ጋር ይደምርልን።
ማሳሰቢያ፦ ካህናት እና አገልጋዮች እንዲሁም ምእመናን በሙሉ ነጭ ልብስ ለብሳችሁ እንድትገኙ በአክብሮት እንጠይቃለን። ወስብሐት ለእግዚአብሔር!
አድራሻ፡ 1350 Buchanan St. NW, Washington, D.C 20011
Via ርእሰ አድባራት ደብረ ሰላም ቅድስት ማርያም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን
"እንግዲህ ሂዱና አሕዛብን ሁሉ በአብ በወልድና በመንፈስ ቅዱስ ስም እያጠመቃችኋቸው ያዘዝኋችሁንም ሁሉ እንዲጠብቁ እያስተማራችኋቸው ደቀ መዛሙርት አድርጓቸው።" ማቴ 28፡19
“የአገልጋይን ሰው ሞት ቸል አትበል ምርር ብለህ አልቅስለት አጽናንተው አዝንለት እንደ ሀገሩ ልማድ አልቅስለት ስለ ሀገሩ ልማድ አንድ ቀን ሁለት ቀን አልቅስለት የብስጭት ሀይል የሚያደክም ስለሆነ ስለ ብስጭት ሀዘን እንዳይገባህ ከዚህ በኋላ ልቅሶህን ተው።” መጽሐፈ ሲራክ 38 16-18
መርሐ ግብር:-
* እሁድ የካቲት 29 ቀን 2018 ዓ.ም (March 8, 2026) በዋሽንግተን ዲሲ እና አካባቢው ሀገረ ስብከት ባሉ አብያተ ክርስቲያናት ጸሎተ ፍትሐት ይደረጋል።
1. እሁድ ከቅዳሴ በኋላ በርእሰ አድባራት ደብረ ሰላም ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን ቅጽረ ግቢ በላይኛው መኪና ማቆሚያ የአካባቢው አድባራት እና ገዳማት አገልጋዮች እና ሕዝበ ክርስቲያኑ ተሰብስበው ሀዘናቸውን ይገልጻሉ።
2. ሰኞ የካቲት 30 ቀን 2018 ዓ.ም (March 9, 2026) ከቀኑ 12pm - 4pm ሰዓት ጀምሮ በላይኛው ትራቨለር ለቅሶ መድረስ ለሚፈልጉ ሁሉ ቦታው ክፍት ይሆናል።
4. ሰኞ ከቀኑ 4:30pm - 7:30pm የአካባቢው አድባራት እና ገዳማት አገልጋዮች እና ሕዝበ ክርስቲያኑ ተሰብስበው በሠርክ ጸሎት እና በትምህርተ ወንጌል፣ በውዳሴ ማርያም ሥነ ሥርዓት ሲዘክሩ ያመሻሉ።
5. ሰኞ ከምሽቱ 7 ሰዓት ክቡር አስከሬኑ ወደ ቤተ ክርስቲያን ይገባል።
6. ከሌሊቱ 1am የአካባቢው አድባራት እና ገዳማት አገልጋዮች እና ሕዝበ ክርስቲያኑ ተሰብስበው በሰዓታት ቆመው ያድራሉ።
7. ማክሰኞ ከጠዋቱ 9am - 12pm የአካባቢው አድባራት እና ገዳማት አገልጋዮች እና ሕዝበ ክርስቲያኑ ተሰብስበው ጸሎተ ፍትሐት ይደረጋል።
8. ማክሰኞ 12pm የመምህር ዘላለም ወንድሙ የሕይወት ታሪክ እና የወዳጅ ዘመድ ምስክርነት ይሰጣል።
9. ማክሰኞ በፓትርያርኩ አጭር ትምህርተ ወንጌል ይሰጣል።
10. ማክሰኞ በሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ በብጹዕ አቡነ ፋኑኤል ቃለ ምዕዳን እና ቡራኬ ተሰጥቶ ክቡር አስከሬኑ ወደ ትውልድ ሀገሩ ኢትዮጵያ ሽኝት ከተደረገ በኋላ ለመታሰቢያ የተዘጋጀው ጸበል ጻዲቅ ተቀምጦ የመርሐ ግብሩ ፍጻሜ ይሆናል። የመምህራችን የወለደ ሰማዕትን ነፍስ ከቅዱሳን ጋር ይደምርልን።
ማሳሰቢያ፦ ካህናት እና አገልጋዮች እንዲሁም ምእመናን በሙሉ ነጭ ልብስ ለብሳችሁ እንድትገኙ በአክብሮት እንጠይቃለን። ወስብሐት ለእግዚአብሔር!
አድራሻ፡ 1350 Buchanan St. NW, Washington, D.C 20011
Via ርእሰ አድባራት ደብረ ሰላም ቅድስት ማርያም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን
3 months ago
የመምህር ዘላለም ወንድሙ (ወለደ ሰማዕት) ክቡር አስከሬን ሽኝትን በተመለከተ የተዘጋጀ መርሐ ግብር
"እንግዲህ ሂዱና አሕዛብን ሁሉ በአብ በወልድና በመንፈስ ቅዱስ ስም እያጠመቃችኋቸው ያዘዝኋችሁንም ሁሉ እንዲጠብቁ እያስተማራችኋቸው ደቀ መዛሙርት አድርጓቸው።" ማቴ 28፡19
“የአገልጋይን ሰው ሞት ቸል አትበል ምርር ብለህ አልቅስለት አጽናንተው አዝንለት እንደ ሀገሩ ልማድ አልቅስለት ስለ ሀገሩ ልማድ አንድ ቀን ሁለት ቀን አልቅስለት የብስጭት ሀይል የሚያደክም ስለሆነ ስለ ብስጭት ሀዘን እንዳይገባህ ከዚህ በኋላ ልቅሶህን ተው።” መጽሐፈ ሲራክ 38 16-18
መርሐ ግብር:-
* እሁድ የካቲት 29 ቀን 2018 ዓ.ም (March 8, 2026) በዋሽንግተን ዲሲ እና አካባቢው ሀገረ ስብከት ባሉ አብያተ ክርስቲያናት ጸሎተ ፍትሐት ይደረጋል።
1. እሁድ ከቅዳሴ በኋላ በርእሰ አድባራት ደብረ ሰላም ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን ቅጽረ ግቢ በላይኛው መኪና ማቆሚያ የአካባቢው አድባራት እና ገዳማት አገልጋዮች እና ሕዝበ ክርስቲያኑ ተሰብስበው ሀዘናቸውን ይገልጻሉ።
2. ሰኞ የካቲት 30 ቀን 2018 ዓ.ም (March 9, 2026) ከቀኑ 12pm - 4pm ሰዓት ጀምሮ በላይኛው ትራቨለር ለቅሶ መድረስ ለሚፈልጉ ሁሉ ቦታው ክፍት ይሆናል።
4. ሰኞ ከቀኑ 4:30pm - 7:30pm የአካባቢው አድባራት እና ገዳማት አገልጋዮች እና ሕዝበ ክርስቲያኑ ተሰብስበው በሠርክ ጸሎት እና በትምህርተ ወንጌል፣ በውዳሴ ማርያም ሥነ ሥርዓት ሲዘክሩ ያመሻሉ።
5. ሰኞ ከምሽቱ 7 ሰዓት ክቡር አስከሬኑ ወደ ቤተ ክርስቲያን ይገባል።
6. ከሌሊቱ 1am የአካባቢው አድባራት እና ገዳማት አገልጋዮች እና ሕዝበ ክርስቲያኑ ተሰብስበው በሰዓታት ቆመው ያድራሉ።
7. ማክሰኞ ከጠዋቱ 9am - 12pm የአካባቢው አድባራት እና ገዳማት አገልጋዮች እና ሕዝበ ክርስቲያኑ ተሰብስበው ጸሎተ ፍትሐት ይደረጋል።
8. ማክሰኞ 12pm የመምህር ዘላለም ወንድሙ የሕይወት ታሪክ እና የወዳጅ ዘመድ ምስክርነት ይሰጣል።
9. ማክሰኞ በፓትርያርኩ አጭር ትምህርተ ወንጌል ይሰጣል።
10. ማክሰኞ በሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ በብጹዕ አቡነ ፋኑኤል ቃለ ምዕዳን እና ቡራኬ ተሰጥቶ ክቡር አስከሬኑ ወደ ትውልድ ሀገሩ ኢትዮጵያ ሽኝት ከተደረገ በኋላ ለመታሰቢያ የተዘጋጀው ጸበል ጻዲቅ ተቀምጦ የመርሐ ግብሩ ፍጻሜ ይሆናል። የመምህራችን የወለደ ሰማዕትን ነፍስ ከቅዱሳን ጋር ይደምርልን።
ማሳሰቢያ፦ ካህናት እና አገልጋዮች እንዲሁም ምእመናን በሙሉ ነጭ ልብስ ለብሳችሁ እንድትገኙ በአክብሮት እንጠይቃለን። ወስብሐት ለእግዚአብሔር!
አድራሻ፡ 1350 Buchanan St. NW, Washington, D.C 20011
ርእሰ አድባራት ደብረ ሰላም ቅድስት ማርያም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን
"እንግዲህ ሂዱና አሕዛብን ሁሉ በአብ በወልድና በመንፈስ ቅዱስ ስም እያጠመቃችኋቸው ያዘዝኋችሁንም ሁሉ እንዲጠብቁ እያስተማራችኋቸው ደቀ መዛሙርት አድርጓቸው።" ማቴ 28፡19
“የአገልጋይን ሰው ሞት ቸል አትበል ምርር ብለህ አልቅስለት አጽናንተው አዝንለት እንደ ሀገሩ ልማድ አልቅስለት ስለ ሀገሩ ልማድ አንድ ቀን ሁለት ቀን አልቅስለት የብስጭት ሀይል የሚያደክም ስለሆነ ስለ ብስጭት ሀዘን እንዳይገባህ ከዚህ በኋላ ልቅሶህን ተው።” መጽሐፈ ሲራክ 38 16-18
መርሐ ግብር:-
* እሁድ የካቲት 29 ቀን 2018 ዓ.ም (March 8, 2026) በዋሽንግተን ዲሲ እና አካባቢው ሀገረ ስብከት ባሉ አብያተ ክርስቲያናት ጸሎተ ፍትሐት ይደረጋል።
1. እሁድ ከቅዳሴ በኋላ በርእሰ አድባራት ደብረ ሰላም ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን ቅጽረ ግቢ በላይኛው መኪና ማቆሚያ የአካባቢው አድባራት እና ገዳማት አገልጋዮች እና ሕዝበ ክርስቲያኑ ተሰብስበው ሀዘናቸውን ይገልጻሉ።
2. ሰኞ የካቲት 30 ቀን 2018 ዓ.ም (March 9, 2026) ከቀኑ 12pm - 4pm ሰዓት ጀምሮ በላይኛው ትራቨለር ለቅሶ መድረስ ለሚፈልጉ ሁሉ ቦታው ክፍት ይሆናል።
4. ሰኞ ከቀኑ 4:30pm - 7:30pm የአካባቢው አድባራት እና ገዳማት አገልጋዮች እና ሕዝበ ክርስቲያኑ ተሰብስበው በሠርክ ጸሎት እና በትምህርተ ወንጌል፣ በውዳሴ ማርያም ሥነ ሥርዓት ሲዘክሩ ያመሻሉ።
5. ሰኞ ከምሽቱ 7 ሰዓት ክቡር አስከሬኑ ወደ ቤተ ክርስቲያን ይገባል።
6. ከሌሊቱ 1am የአካባቢው አድባራት እና ገዳማት አገልጋዮች እና ሕዝበ ክርስቲያኑ ተሰብስበው በሰዓታት ቆመው ያድራሉ።
7. ማክሰኞ ከጠዋቱ 9am - 12pm የአካባቢው አድባራት እና ገዳማት አገልጋዮች እና ሕዝበ ክርስቲያኑ ተሰብስበው ጸሎተ ፍትሐት ይደረጋል።
8. ማክሰኞ 12pm የመምህር ዘላለም ወንድሙ የሕይወት ታሪክ እና የወዳጅ ዘመድ ምስክርነት ይሰጣል።
9. ማክሰኞ በፓትርያርኩ አጭር ትምህርተ ወንጌል ይሰጣል።
10. ማክሰኞ በሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ በብጹዕ አቡነ ፋኑኤል ቃለ ምዕዳን እና ቡራኬ ተሰጥቶ ክቡር አስከሬኑ ወደ ትውልድ ሀገሩ ኢትዮጵያ ሽኝት ከተደረገ በኋላ ለመታሰቢያ የተዘጋጀው ጸበል ጻዲቅ ተቀምጦ የመርሐ ግብሩ ፍጻሜ ይሆናል። የመምህራችን የወለደ ሰማዕትን ነፍስ ከቅዱሳን ጋር ይደምርልን።
ማሳሰቢያ፦ ካህናት እና አገልጋዮች እንዲሁም ምእመናን በሙሉ ነጭ ልብስ ለብሳችሁ እንድትገኙ በአክብሮት እንጠይቃለን። ወስብሐት ለእግዚአብሔር!
አድራሻ፡ 1350 Buchanan St. NW, Washington, D.C 20011
ርእሰ አድባራት ደብረ ሰላም ቅድስት ማርያም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን
Sponsored by
Surafel
3 months ago
Yederaw Support:
በራሱ ቀብር ላይ የተገኘው ደራሲ
#ethiopia | መንግሥቱ የተወለደው በ 1920 ዓ.ም በቀድሞው የሲዳሞ ክፍለ ሐገር፣ በቡሬ ገጠራማ መንደር ውስጥ ነው። የቤተሰቦቹ ሕይወት በግብርና ስራ ላይ የተመሰረተ ስለነበር መንግሥቱም ገና በልጅነቱ የወላጆቹን ስራ በአቅሙ ያግዝ ነበር። የመንግሥቱ ሕይወት በፈተና የተሞላች መሆን የጀመረችው ገና በማለዳው ነበር።
በዚያው የልጅነት እድሜው እባብ ነድፎት ለስድስት ሳምንታት ያህል ሕሊናውን ስቶ ከሰነበተ በኋላ ከሞት ተረፈ።
ፋሺስት ኢጣሊያ ኢትዮጵያን በወረረበት ወቅት የመንግሥቱን የትውልድ መንደር ሲያቃጥል መንግሥቱ ከእሳቱ የተረፈው በተዓምር ነበር። ቤታቸው ሲቃጠል መንግስቱ የሚሄድበት አጥቶ በቤት ውስጥ ይቅበዘበዝ ነበር። በሚቃጠለው በነመንግስቱ ቤት ወስጥ ሰው መኖሩን የተረዳ አንድ የአካባቢው ሰው ወደ ቤቱ ውስጥ በመግባት መንግሥቱን ከሞት አተረፈው።
በፋሺስቶች መምጣት የተደናገጠው የአካባቢው ሰው ቤቱን ትቶ ሲሸሽ ፈረስ መጋለብ የማይችለው መንግሥቱ በፈረስ ሊያመልጥ ወሰነና ከፈረስ ላይ ወጣ። የፈረሱ ፍጥነት አስደንግጦት ከፈረሱ ላይ ለመውረድ ወሰነ፤ ለስላሳ መሬት አገኘሁ ብሎ ከፈረሱ ላይ ተፈናጥሮ ሲወርድ ድንጋይ ላይ ቢወድቅም ከሞት መትረፍ ችሏል።
የሞትን ደጅ እየረገጡ መመለስ የተለማመደው መንግሥቱ በአንድ ወቅት በከብት ጥበቃ ላይ ሳለ ጅብ ተሸክሞት ሊሄድ ሲታገለው የለበሰውን ደበሎ ለጅቡ ሰጥቶ ማምለጥ ችሏል። ለዚህም ነው መንግሥቱን ከልጅነቱ ጀምረው የሚያውቁት ሰዎች ‹‹ሕይወቱ በሙሉ የፈተና ዘመን ነበር›› ብለው የሚመሰክሩት።
መንግሥቱ እድሜው ለትምህርት ሲደርስ ተፈሪ መኮንን ትምህርት ቤት ገብቶ ፊደል መቁጠር ቻለ። ከፍ ሲልም በወታደርነት ለማገልገል ተመዘገበ። በውትድርናው ግን አልገፋበትም። ከውትድርናው ዓለም ወጥቶ በፖስታና ቴሌፎን ሚኒስቴር ውስጥ ተቀጠረ ። በስራው የተመሰገነ ታታሪ ሰራተኛ ስለነበርም በአጭር ጊዜ ውስጥ እድገት አግኝቶ ወደ ድሬዳዋ ተዛወረ።
ደመወዙ ግን አጥጋቢ ስላልሆነለት ስራውን ለቆ በእጥፍ ደመወዝ በምድር ባቡር ኩባንያ ውስጥ ተቀጠረ። የፖስታና ቴሌፎን ሚኒስቴር ይህን የመንግሥቱን ድርጊት ሲሰማ ወደ ቀድሞ ስራው በግዳጅ መለሰው። መንግሥቱ ግን ለአለቆቹ ውሳኔ የሚመች አልሆነም። ‹‹አለቃም ይሁን ምንዝር በእጄ ከመጥፋቱ በፊት በሰላም አሰናብቱኝ›› ብሎ አስፈራራቸው። ይህ ፉከራው ሳያዋጣው ስለቀረ ሌላ መላ ዘየደ። ‹‹ራሴን አጠፋለሁ›› ብሎ ማስፈራራት የመንግሥቱ ሌላኛው ዘዴ ነበር። እንዳጋጣሚ ሆኖ ይህኛው መላ ሰራለትና መስሪያ ቤቱ ‹‹ ራስህን ከምታጠፋ እንለቅሃለን›› ብሎ አሰናበተው።
ወደ ምድር ባቡር ኩባንያ ሄዶ ለጥቂት ጊዜያት ያህል ከሰራ በኋላ ‹‹የኩባንያው ስራ አስኪያጅ እብሪት አስመረረኝ›› በማለት ስራውን በፈቃዱ ለቀቀ። ጥቂት ሰንብቶ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በጥሩ ደመወዝ በመዝገብ ቤት ሹምነት ተቀጠረ። በመዝገብ ቤት ሹምነት ጥቂት ከሰራ በኋላ ወደ ትርጉም ክፍል ተዛወረ። ከዚያም ወደ ባንኩ አስተዳደር ክፍል ስልጣን ቢጤ አገኘ።
በወቅቱ ሁለት ጊዜያት ያህል ጥሩ የደመዝ ጭማሪ ማግኘት ችሏል። ጭማሪዎቹን ያገኘበት መንገድ ግን የተለየ ነበር። ይኸውም ሕንዳዊውን የባንኩን ሥራ አስኪያጅ በሽጉጥ በማስፈራራት ነበር። ሌላ አጋጣሚ ተፈጥሮ ሳይሳካ ቀረ እንጂ መንግሥቱ ከሽጉጥ ተሻግሮ በናስማስር ጠመንጃ በማስፈራራት ሦስተኛ ጭማሪ ለማስደረግ እየተዘጋጀ ነበር።
‹‹ባሕል አስከብራለሁ›› በሚል ምክንያት በርኖስ እየለበሰ ቢሮ መግባት ጀምሮም ነበር። በዚህም ተከሶ ማስጠንቀቂያ ተሰጥቶት በብዙ ልመና በርኖሱን አወ ለቀ። በዚህ የተናደደው መንግሥቱ ባንኩን በጋዜጣ ጽሑፍ ሙልጭ አድርጎ ተሳደበ። ይባስ ብሎም ንጉሠ ነገሥት ቀዳማዊ አፄ ኃይለሥላሴ የባንኩን አገልግሎትና አሰራር ሊጎበኙ ወደ ባንኩ በሄዱበት ወቅት መንግሥቱ ወደ ክፍሉ ደብቆ ያስገባው ተጣጣፊ አልጋ ላይ ተኝቶ ተገኘ። ለምን ቢሮ ውስጥ እንደተኛ ሲጠየቅም ‹‹አለቆቼ ስራ ስለማይሰጡኝ የምሰራው ስራ ሳይኖር በከንቱ ደመወዝ እንደሚከፈለኝ ለማሳወቅ ነው›› ብሎ ተናገረ። በዚህ አድራጎቱ የተበሳጩት አለቆቹ በማግሥቱ የስንብት ደብዳቤ በፖሊስ እጅ ደረሰው።
በባንኩ የሥራ ኃላፊዎች ውሳኔ ያልተስማማው መንግሥቱ መስሪያ ቤቱ ላይ ክስ መሰረተ። መንግሥቱ መስሪያ ቤቱን አሸነፈ። ነገር ግን ጉዳዩን ተከታትሎ ሳያስፈፅም በማስታወቂያ ሚኒስቴር በጋዜጠኛነት ተቀጠረ። በዚህኛው መሥሪያ ቤት የመንግሥቱ መንፈስ የተረጋጋ መሰለ። በወቅቱ በጋዜጣ ላይ በሚያቀርባቸው ጽሑፎቹ በብዙዎች ዘንድ እውቅና ለማግኘት በቃ። መንግሥቱ በወቅቱ በጽሑፎቹ ይዳስሳቸው የነበሩት ርዕሰ ጉዳዮች አብዛኞቹ የሥራ ባልደረቦቹ የማይደፍሯቸው ነበሩ።
በጋዜጠኝነት የጀመረው ጽሑፍ ወደ ደራሲነት አሸጋገረው። የድርሰት ስራውን የጀመረው በማስታወቂያ ሚኒስቴር ውስጥ በጋዜጠኛነት ተቀጥሮ ማገልገል ከጀመረ ወዲህ ነበር። የመጀመሪያ ስራውንም ‹‹ሌላው እንደሚያይህ›› በተሰኘ ርዕስ በ 1949 ዓ.ም ለአንባቢያን አደረሰ። መጽሐፉ ልብ ወለድ ሲሆን ከጋዜጠኝነት ወደ ደራሲነት የተሸጋገረበት የበኩር ስራው ነው። ከዚህ በኋላ ብዙ መጽሐፍትን መጻፍ ችሏል።
‹‹ከማን አንሼ›› የተሰኘችው የልብ ወለድ መጽሐፉ የፊት ሽፋኗ ላይ አህያ ሙሉ ሱፍ ከነሰደርያውና ካፖርት ደርባ፣ ባርኔጣ ደፍታ፣ መነጽር አጥልቃ ትታይበታለች። ድርሰቱ በአህያዪቱ ዙሪያ የሚያጠነጥን ሲሆን የመጽሐፏ አንዱ ክፍል የአህያ ጸሎት ነበር። ‹‹በስመ ጎርማንዴዎስ ወሰርዶ ወፋንድያ›› በማለት ጸሎቷን አድርሳ ወደ ቀለቧ እንደምታመራ ተጠቅሷል። አንድ ሰው እጅ እንዲነሳት ተደርጋ የተሳለችው አህያ ‹‹የወቅቱን የፓርላማ አባላት ለመሳደብ ሆን ብሎ ያዘጋጃት ናት›› ይባላል። ከላይ ከተጠቀሱት ሥራዎቹ በተጨማሪ የትርጉም መጽሐፍትንም ለአንባቢያን አድርሷል።
መንግሥቱ ገዳሙ ጥሩ ጸሐፊ ብቻም ሳይሆን ጥሩ አንባቢም ነበር። በመኖሪያ ቤቱ ውስጥ ድንቅ ቤተ-መጽሐፍት አደራጅቶ ነበር። መንግሥቱ ራሱን በራሱ የፈጠረ ምሁር ነበር። በመደበኛ ትምህርት ብዙም ባይገፋም በእንግሊዝኛ ቋንቋ ጭምር መጽሐፍ (‹‹The Psychology of The White Races››) መጻፍ ችሎ ነበር። ለአንድ ዓመት ሥራ ሲፈታ ግን መጽሐፍቱን በሙሉ ቸበቸባቸው። ከዚያ ጊዜ በኋላም የመጽሐፍት ድሃ እንደሆነ ይነገራል።
መንግሥቱ በማስታወቂያ ሚኒስቴር ውስጥ የቆየው ለ15 ዓመታት ያህል ቢሆንም ያቀርባቸው የነበሩት ጋዜጣዊ ጽሑፎች ግን ጥቂት የሚባሉ ነበሩ። ብዕሩን ሲያነሳ ግን ‹‹ጉድ ለማውጣት›› ነበር። በወቅቱ የሚከናወኑና ከባለስልጣናትም ሆነ ከሌላው የኅብረተሰብ ክፍል የተደበቁ ነገሮችን ይፋ ለማውጣት የመንግሥቱ ብዕር ደፋር ነበረች።
‹‹ሞገደኛ›› የሚል ስያሜ የተሰጠውም ከግላዊ ባሕርይውና ድርጊቱ ባሻገር በሙያዊ ተግባሩ ሞጋች ስለነበር ነው። ጽሑፎቹ የሕዝቡን እውነተኛ ሕይወት የሚዳስሱ እንዲሁም ችግሩንና በደሉን ከፍላጐቱ ጋር የሚያመለክቱ ነበሩ። በተለይም የሥርዓቱን ንቅዘት በመዋጋት የሚደርስበት አሳርና መከራ ከሙያው አላገደውም። መንግስቱ ‹‹የኢትዮጵያ ጋዜጠኞች የገና ዳቦ ናቸው›› ሲል ብዙ ጊዜ ተናግሯል።
መንግሥቱ የማተሚያ ቤት እዳ መክፈል ተስኖት ሲሰቃይ ቢሸጡ ኖሮ ከማተሚያ ቤቱ እዳ የሚበልጥ ገንዘብ ሊያወጡ የሚችሉ መጽሐፍቱን ለየድርጅቶቹ በነፃ ያድል እንዲሁም ለመጻሕፍት አዟሪዎችም በነፃና በዱቤ ይሰጥ ነበር። ስለአብዛኞቹ መጽሐፍቱ ይዘት ግን አያስታውስም ነበር፤ የመጽሐፍቱ ቅጂም ኖሮት አያውቅም ነበር ይባላል። ስለመንግሥቱ ገዳሙ ሲነሳ አብሮ የሚታወሰው አወዛጋቢና አስቂኝ ባህርያቱ እንዲሁም በፈተና የተሞላው የሕይወት ጉዞው ናቸው። የመንግሥቱ ሕይወት በሙሉ ውጣ ውረድ የበዛበት ነበር። የሚሰራቸው ነገሮች አብዛኞቹ የሚያስደምሙና የሚያስቁ ነበሩ። ከላይ ከተጠቀሱት አለቆቹን የማስፈራራትና የመናቅ ድርጊቶቹ በተጨማሪ ሌሎች አስገራሚ ባህርያቱንና ድርጊቶቹን በጥቂቱ እንመልከት።
በአንድ ወቅት ለስራ ጉዳይ ወደ አስመራ ይላካል። ታዲያ በየፖሊስ ጣቢያው ስለሚገኙት ማረሚያ ቤቶች ሁኔታ መጻፍ ፈለገ። ባለስልጣኑን ለማስፈቀድ ቢሞክርም ሳይሳካለት ቀረ። ሞገደኛው መንግሥቱ ግን ወንጀል ሰርቶ ፖሊስ ጣቢያ መግባትን ለዓላማው ማሳኪያ አድርጎ ሊጠቀምበት አሰበ። ወደ አንድ መጠጥ ቤት ጎራ ይልና ባዶ ጠርሙሶችን እየመረጠ መሰባበር ጀመረ።
ኡኡታው ቀለጠና ፖሊስ እያዳፋ ወደ ፖሊስ ጣቢያ ወሰደው። ከሦስት ቀናት በኋላ በዋስ ተለቆ አዲስ አበባ ሲመለስ ስለአስመራ ፖሊስ ጣቢያዎች በርከት ያሉ መጣጥፎችን መፃፍ ቻለ። የአዲስ አበባን ፖሊስ ጣቢያዎች ለመጎብኘት ስላቀደ ሌላ አምባጓሮ ፈጥሮ ፖሊስ ጣቢያዎቹን በእስረኛነት ጎብኝቷቸዋል።
መንግሥቱ አንዱን ምስኪን ፈረንጅ በ700 ብር ደመወዝ ቀጥሮ ካፖርት እያሸከመ በፒያሳ ይዞር ነበር። ይህም ‹‹ፈረንጅ የሐበሻ አሽከር አይሆንም›› የሚለው አመለካከት ስህተት መሆኑን በተግባር ለማሳየት ነበር።
4 ኪሎ አካባቢ አንድ ተወዳጅ ውስኪ ቤት ነበር። ታዲያ የውስኪ ወዳጆች ቤቱን ከአፍ እስከገደፉ ድረስ እየሞሉት መቀመጫ አይገኝም ነበር። አንድ ቀን መንግሥቱ ከአንድ የውጭ ጋዜጠኛ ጋር ውስኪ ለመጠጣት ወደ ውስኪ ቤቱ ሲሄድ እንኳን መቀመጫ መቆሚያም ይጠፋል። መንግሥቱ በሩ ላይ ቆሞ አጨበጨበ።
ጠጪው ሁሉ ፀጥ ሲል በወቅቱ የነበሩትን ጠቅላይ ሚኒስትር አክሊሉ ሀብተወልድን ጨምሮ ብዙ የመንግሥት ሹማምንትን ስም እያነሳ መሳደብ ጀመረ። ምድረ ጠጪም ‹‹የመንግሥቱ ስድብ ያሳፍሰናል›› በሚል ስጋት ሂሳቡን እየከፈለ ቤቱን ለቆ ወጣ። ቤቱ ጭር ሲል መንግሥቱ ከወዳጁ ጋር ምቹ ሶፋ ላይ ተቀምጦ ውስኪን መጠጣት ጀመረ።
መንግስቱ ገዳሙ አንጋፋ ጠጪ በመባል የሚታወቅ ሲሆን ለምን እንደሚጠጣ ሲጠየቅ፤ ‹‹እኔ እኮ ለምን እንደምጠጣ እናንተ ደንቆሮዎች ስለሆናችሁ አይገባችሁም፤ የእኔ አእምሮ ከተራው ሰው አእምሮ በጣም የላቀ ነው። ስለዚህ ከእናንተ ጋር ለመነጋገር ያንን ከፍተኛ አእምሮዬን ወደ እናንተ ደረጃ ላወርደው የምችለው በአልኮል ኃይል ነው›› በማለት መናገሩ ይታወሳል።
መንግሥቱ ከጽሑፉና ከንግግሩ ባሻገር በእለታዊ ድርጊቱ ሁሉ ሥርዓቱን ይቃወም ነበር። አንዲት አህያ ጆሮዋ ላይ ብር ለጥፎ በየመጠጥ ቤቱ እየዞረ፣ አስተናጋጆቹ እንዲታዘዟት ያደርግ ነበር። በዚህም የጊዜው ባለስልጣኖች በገንዘብ እንጂ በአስተሳሰብ ከአህያ እንደማይሻሉ ለማስረዳት ያደረገው ነው ተብሏል።
አህያዋን ይዟት በየቦታው ሲዞር ‹‹ምንድን ነች?›› ብለው ሲጠይቁትም ‹‹የማስታወቂያ ሚኒስቴር ባልደረባ ነች›› እያለ ይመልስ እንደነበር ይወሳል፤ በዚያ ዘመን ማስታወቂያውን በአህያ እየዞረ የሚያስነግረው ብሔራዊ ሎተሪ፤ በማስታወቂያ ሚኒስቴር ሥር ነበር። በመንግሥቱ እሳቤ አህያዋ የባለስልጣኖች ተምሳሌት ነበረች። የ 1953 ዓ.ም የመፈንቅለ መንግሥት ሙከራን ደግፎ ሕዝቡን መቀስቀሱም ስርዓቱን የመቃወሙ ምልክት ነበር።
በሌላ ጊዜ ደግሞ በመስሪያ ቤቱ ግብዣ ላይ የአለቃው አለቃ ባለመገኘታቸው ይወርፋቸዋል። ድርጊቱ ‹‹ክብረ ነክ›› ተብሎ በማግሥቱ ኮሚቴ ተቋቁሞ ለፍርድ ቀረበ። ጥፋቱን የፈጸመበትን ምክንያት እንዲያብራራ ሲጠየቅ ‹‹ሰዎች ገፋፍተውኝ ነው›› ብሎ መለሰ።
እነማን እንደሆኑ ሲጠየቅም ለፍርድ የተሰየሙትን አባላት ስም ጠቀሰ። በዚህ የተነሳ የኮሚቴው አባላት ዳኝነቱን ትተው መንግሥቱን ለመደብደብ ከጀሉ። መንግሥቱ ሮጦ ወጣ፤ የተናደዱት የኮሚቴው አባላት ግን ተከትለው ያባር ሩታል። መንግሥቱ የኮሚቴው አባላት ስሜታቸውን መቆጣጠር የሚችሉ አለመሆናቸውን በአደባባይ አሳየ።
ሌላ ጊዜ ደግሞ መንግሥቱን ሮም ከተማን እንዲጎበኝ ተጋበዘ። መንጌ ትኬቱን፣ ፓስፖርቱንና ቪዛውን በእጁ ካስገባ በኋላ በበረራው ዋዜማ ቀን ወደ አለቃው ዘንድ ሄዶ ከሳምንት በኋላ ወደ አውሮፓ እንደሚሄድና ጉዞውን እንዲፈቅዱለትም አንጀት የሚበላ ደብዳቤ ፅፎ ሰጣቸው።
አለቃውም የሚያስቸግራቸው ሰራተኛቸው በእጃቸው ላይ መውደቁ አስደስቷቸው ‹‹ደብዳቤው ከማኅደሩ ጋር ተያይዞ ይቀመጥ›› የሚል ትዕዛዝ ጽፈው ማመልከቻውን ወደ መዝገብ ቤት ላኩት። መንግሥቱ እንደተጫወተባቸው አለቃው ያወቁት ጠዋት ለስራ ሲፈልጉት በዚያው ቀን ጠዋት ቀደም ብሎ ወደ ሮም መብረሩ ሲነገራቸው ነበር።
ሌላኛው የመንግሥቱ ጠባይ አምባጓሮ መውደዱ ነበር። በዚህም ጠባዩ ምክንያት ከመቶ ጊዜ በላይ ተቧቅሷል። አራት ጊዜ በጩቤ ተወግቷል፤ አራት ጊዜ በመኪና ተገጭቷል፤ ህሊናውን እስከሚስት ድረስ ያጋ ጠመውን ጨምሮ 20 ጊዜ ማጅራቱን በወሮበላዎች ተመትቷል። አንድ ሙሉ ሌሊት በቆሻሻ ክምር ላይ አሳልፏል።
አንድ መ/ቤት እየሰራ እያለ አለቃው ዕድገት አግኝተው ወደ ሌላ ቦታ ሲሄዱ የሽኝት ፕሮግራም ይዘጋጅላቸዋል። ለፕሮግራሙ ከሁሉም ሰራተኞች የበለጠ መዋጮ አዋጣ። "ለምን ይሆን ይሄን ያደረከው?" ተብሎ ሲጠየቅ "አለቃዬ እዚህ እንዳይቀር ብሎም ወደዚህ ተመልሶ እንዳይመጣ ነው።" በማለት አስገራሚ መልስ ሰጥቷል።
መንግሥቱ በራሱ ላይ መቀለድም ይወድ ነበር። አንድ ጊዜ ሳይሞት ‹‹ሞቻለሁ›› ብሎ በሌላ ሰው በኩል በማስነገር ወደ መስሪያ ቤቱ ስልክ አስደውሎ የቀብሩ ቦታ ቀጨኔ መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን እንደሆነ አሳወቀ። ለቀስተኛው በቤተ-ክርስቲያኑ ተገኝቶ ተሰብስቦ አስከሬን ሲጠብቅ መንግሥቱ ጥቁር ሱፉን ግጥም አድርጎና ባርኔጣውን ደፍቶ ብቅ አለ። ለቀስተኛውን አመስግኖ ሳይሞት ‹‹ሞቻለሁ›› ብሎ ያስነገረው በእውነት ቢሞት የቀብሩ ስነ ስርዓት ምን እንደ ሚመስል በቁሙ ለማየት ፈልጎ ያደረገው መሆኑን ገለፆ ለቀስተኛውን በተነ።
መንግሥቱ በዓለም ዙሪያ ታዋቂ ሰዎችን በሚመዘግበው የ‹‹Who is Who›› ባሕረ መዝገብ ውስጥ ስሙ ሰፍሮለታል። ‹‹ትዳርን ለምርምር የሚጠቀምበት ይመስላል›› እስከሚባል ድረስ አራት ጊዜ አግብቶ አራት ጊዜ ፈትቷል።
መንግስቱ ሊሞት አንድ ሳምንት ሲቀረው "መንግስቱ ገዳሙ ሰሞኑን ይሞታል" እያለ በራሱ ላይ አሟርቶ በተወለደ በ48 ዓመቱ በተናገረው ሳምንቱ ውስጥ ሐምሌ 29 ቀን 1977 ዓ/ም ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል።
ከስራዎቹ መካከልም፡-
-- አመፀኛ ሞግዚት -- እንኮዬ ደማሜ
-- ብታምንም ባታምንም -- ኮሳሳው ተማሪ
-- የእንስሳት ሮኬት -- ፃድቁ አራምዴ
-- ማጅራት መቺ -- አሳማና ድመት
-- ከምሱር -- አንተ ማን ነህ
-- የሃምሳ አለቃ ገብሬ -- አመሰግንሻለሁ
-- The Psychology of The White Races
-- የአልማዝ እዳ
-- ከማን አንሼ .....… የሚሉት ይጠቀሳሉ።
አዲስ ዘመን (መጋቢት 22 ቀን 2013)
ተጨማሪ የተለያዩ ማኅበራዊ ገጾች
Via #ሙክታሮቪች
#getutemesgen #getu #ጌጡ
በራሱ ቀብር ላይ የተገኘው ደራሲ
#ethiopia | መንግሥቱ የተወለደው በ 1920 ዓ.ም በቀድሞው የሲዳሞ ክፍለ ሐገር፣ በቡሬ ገጠራማ መንደር ውስጥ ነው። የቤተሰቦቹ ሕይወት በግብርና ስራ ላይ የተመሰረተ ስለነበር መንግሥቱም ገና በልጅነቱ የወላጆቹን ስራ በአቅሙ ያግዝ ነበር። የመንግሥቱ ሕይወት በፈተና የተሞላች መሆን የጀመረችው ገና በማለዳው ነበር።
በዚያው የልጅነት እድሜው እባብ ነድፎት ለስድስት ሳምንታት ያህል ሕሊናውን ስቶ ከሰነበተ በኋላ ከሞት ተረፈ።
ፋሺስት ኢጣሊያ ኢትዮጵያን በወረረበት ወቅት የመንግሥቱን የትውልድ መንደር ሲያቃጥል መንግሥቱ ከእሳቱ የተረፈው በተዓምር ነበር። ቤታቸው ሲቃጠል መንግስቱ የሚሄድበት አጥቶ በቤት ውስጥ ይቅበዘበዝ ነበር። በሚቃጠለው በነመንግስቱ ቤት ወስጥ ሰው መኖሩን የተረዳ አንድ የአካባቢው ሰው ወደ ቤቱ ውስጥ በመግባት መንግሥቱን ከሞት አተረፈው።
በፋሺስቶች መምጣት የተደናገጠው የአካባቢው ሰው ቤቱን ትቶ ሲሸሽ ፈረስ መጋለብ የማይችለው መንግሥቱ በፈረስ ሊያመልጥ ወሰነና ከፈረስ ላይ ወጣ። የፈረሱ ፍጥነት አስደንግጦት ከፈረሱ ላይ ለመውረድ ወሰነ፤ ለስላሳ መሬት አገኘሁ ብሎ ከፈረሱ ላይ ተፈናጥሮ ሲወርድ ድንጋይ ላይ ቢወድቅም ከሞት መትረፍ ችሏል።
የሞትን ደጅ እየረገጡ መመለስ የተለማመደው መንግሥቱ በአንድ ወቅት በከብት ጥበቃ ላይ ሳለ ጅብ ተሸክሞት ሊሄድ ሲታገለው የለበሰውን ደበሎ ለጅቡ ሰጥቶ ማምለጥ ችሏል። ለዚህም ነው መንግሥቱን ከልጅነቱ ጀምረው የሚያውቁት ሰዎች ‹‹ሕይወቱ በሙሉ የፈተና ዘመን ነበር›› ብለው የሚመሰክሩት።
መንግሥቱ እድሜው ለትምህርት ሲደርስ ተፈሪ መኮንን ትምህርት ቤት ገብቶ ፊደል መቁጠር ቻለ። ከፍ ሲልም በወታደርነት ለማገልገል ተመዘገበ። በውትድርናው ግን አልገፋበትም። ከውትድርናው ዓለም ወጥቶ በፖስታና ቴሌፎን ሚኒስቴር ውስጥ ተቀጠረ ። በስራው የተመሰገነ ታታሪ ሰራተኛ ስለነበርም በአጭር ጊዜ ውስጥ እድገት አግኝቶ ወደ ድሬዳዋ ተዛወረ።
ደመወዙ ግን አጥጋቢ ስላልሆነለት ስራውን ለቆ በእጥፍ ደመወዝ በምድር ባቡር ኩባንያ ውስጥ ተቀጠረ። የፖስታና ቴሌፎን ሚኒስቴር ይህን የመንግሥቱን ድርጊት ሲሰማ ወደ ቀድሞ ስራው በግዳጅ መለሰው። መንግሥቱ ግን ለአለቆቹ ውሳኔ የሚመች አልሆነም። ‹‹አለቃም ይሁን ምንዝር በእጄ ከመጥፋቱ በፊት በሰላም አሰናብቱኝ›› ብሎ አስፈራራቸው። ይህ ፉከራው ሳያዋጣው ስለቀረ ሌላ መላ ዘየደ። ‹‹ራሴን አጠፋለሁ›› ብሎ ማስፈራራት የመንግሥቱ ሌላኛው ዘዴ ነበር። እንዳጋጣሚ ሆኖ ይህኛው መላ ሰራለትና መስሪያ ቤቱ ‹‹ ራስህን ከምታጠፋ እንለቅሃለን›› ብሎ አሰናበተው።
ወደ ምድር ባቡር ኩባንያ ሄዶ ለጥቂት ጊዜያት ያህል ከሰራ በኋላ ‹‹የኩባንያው ስራ አስኪያጅ እብሪት አስመረረኝ›› በማለት ስራውን በፈቃዱ ለቀቀ። ጥቂት ሰንብቶ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በጥሩ ደመወዝ በመዝገብ ቤት ሹምነት ተቀጠረ። በመዝገብ ቤት ሹምነት ጥቂት ከሰራ በኋላ ወደ ትርጉም ክፍል ተዛወረ። ከዚያም ወደ ባንኩ አስተዳደር ክፍል ስልጣን ቢጤ አገኘ።
በወቅቱ ሁለት ጊዜያት ያህል ጥሩ የደመዝ ጭማሪ ማግኘት ችሏል። ጭማሪዎቹን ያገኘበት መንገድ ግን የተለየ ነበር። ይኸውም ሕንዳዊውን የባንኩን ሥራ አስኪያጅ በሽጉጥ በማስፈራራት ነበር። ሌላ አጋጣሚ ተፈጥሮ ሳይሳካ ቀረ እንጂ መንግሥቱ ከሽጉጥ ተሻግሮ በናስማስር ጠመንጃ በማስፈራራት ሦስተኛ ጭማሪ ለማስደረግ እየተዘጋጀ ነበር።
‹‹ባሕል አስከብራለሁ›› በሚል ምክንያት በርኖስ እየለበሰ ቢሮ መግባት ጀምሮም ነበር። በዚህም ተከሶ ማስጠንቀቂያ ተሰጥቶት በብዙ ልመና በርኖሱን አወ ለቀ። በዚህ የተናደደው መንግሥቱ ባንኩን በጋዜጣ ጽሑፍ ሙልጭ አድርጎ ተሳደበ። ይባስ ብሎም ንጉሠ ነገሥት ቀዳማዊ አፄ ኃይለሥላሴ የባንኩን አገልግሎትና አሰራር ሊጎበኙ ወደ ባንኩ በሄዱበት ወቅት መንግሥቱ ወደ ክፍሉ ደብቆ ያስገባው ተጣጣፊ አልጋ ላይ ተኝቶ ተገኘ። ለምን ቢሮ ውስጥ እንደተኛ ሲጠየቅም ‹‹አለቆቼ ስራ ስለማይሰጡኝ የምሰራው ስራ ሳይኖር በከንቱ ደመወዝ እንደሚከፈለኝ ለማሳወቅ ነው›› ብሎ ተናገረ። በዚህ አድራጎቱ የተበሳጩት አለቆቹ በማግሥቱ የስንብት ደብዳቤ በፖሊስ እጅ ደረሰው።
በባንኩ የሥራ ኃላፊዎች ውሳኔ ያልተስማማው መንግሥቱ መስሪያ ቤቱ ላይ ክስ መሰረተ። መንግሥቱ መስሪያ ቤቱን አሸነፈ። ነገር ግን ጉዳዩን ተከታትሎ ሳያስፈፅም በማስታወቂያ ሚኒስቴር በጋዜጠኛነት ተቀጠረ። በዚህኛው መሥሪያ ቤት የመንግሥቱ መንፈስ የተረጋጋ መሰለ። በወቅቱ በጋዜጣ ላይ በሚያቀርባቸው ጽሑፎቹ በብዙዎች ዘንድ እውቅና ለማግኘት በቃ። መንግሥቱ በወቅቱ በጽሑፎቹ ይዳስሳቸው የነበሩት ርዕሰ ጉዳዮች አብዛኞቹ የሥራ ባልደረቦቹ የማይደፍሯቸው ነበሩ።
በጋዜጠኝነት የጀመረው ጽሑፍ ወደ ደራሲነት አሸጋገረው። የድርሰት ስራውን የጀመረው በማስታወቂያ ሚኒስቴር ውስጥ በጋዜጠኛነት ተቀጥሮ ማገልገል ከጀመረ ወዲህ ነበር። የመጀመሪያ ስራውንም ‹‹ሌላው እንደሚያይህ›› በተሰኘ ርዕስ በ 1949 ዓ.ም ለአንባቢያን አደረሰ። መጽሐፉ ልብ ወለድ ሲሆን ከጋዜጠኝነት ወደ ደራሲነት የተሸጋገረበት የበኩር ስራው ነው። ከዚህ በኋላ ብዙ መጽሐፍትን መጻፍ ችሏል።
‹‹ከማን አንሼ›› የተሰኘችው የልብ ወለድ መጽሐፉ የፊት ሽፋኗ ላይ አህያ ሙሉ ሱፍ ከነሰደርያውና ካፖርት ደርባ፣ ባርኔጣ ደፍታ፣ መነጽር አጥልቃ ትታይበታለች። ድርሰቱ በአህያዪቱ ዙሪያ የሚያጠነጥን ሲሆን የመጽሐፏ አንዱ ክፍል የአህያ ጸሎት ነበር። ‹‹በስመ ጎርማንዴዎስ ወሰርዶ ወፋንድያ›› በማለት ጸሎቷን አድርሳ ወደ ቀለቧ እንደምታመራ ተጠቅሷል። አንድ ሰው እጅ እንዲነሳት ተደርጋ የተሳለችው አህያ ‹‹የወቅቱን የፓርላማ አባላት ለመሳደብ ሆን ብሎ ያዘጋጃት ናት›› ይባላል። ከላይ ከተጠቀሱት ሥራዎቹ በተጨማሪ የትርጉም መጽሐፍትንም ለአንባቢያን አድርሷል።
መንግሥቱ ገዳሙ ጥሩ ጸሐፊ ብቻም ሳይሆን ጥሩ አንባቢም ነበር። በመኖሪያ ቤቱ ውስጥ ድንቅ ቤተ-መጽሐፍት አደራጅቶ ነበር። መንግሥቱ ራሱን በራሱ የፈጠረ ምሁር ነበር። በመደበኛ ትምህርት ብዙም ባይገፋም በእንግሊዝኛ ቋንቋ ጭምር መጽሐፍ (‹‹The Psychology of The White Races››) መጻፍ ችሎ ነበር። ለአንድ ዓመት ሥራ ሲፈታ ግን መጽሐፍቱን በሙሉ ቸበቸባቸው። ከዚያ ጊዜ በኋላም የመጽሐፍት ድሃ እንደሆነ ይነገራል።
መንግሥቱ በማስታወቂያ ሚኒስቴር ውስጥ የቆየው ለ15 ዓመታት ያህል ቢሆንም ያቀርባቸው የነበሩት ጋዜጣዊ ጽሑፎች ግን ጥቂት የሚባሉ ነበሩ። ብዕሩን ሲያነሳ ግን ‹‹ጉድ ለማውጣት›› ነበር። በወቅቱ የሚከናወኑና ከባለስልጣናትም ሆነ ከሌላው የኅብረተሰብ ክፍል የተደበቁ ነገሮችን ይፋ ለማውጣት የመንግሥቱ ብዕር ደፋር ነበረች።
‹‹ሞገደኛ›› የሚል ስያሜ የተሰጠውም ከግላዊ ባሕርይውና ድርጊቱ ባሻገር በሙያዊ ተግባሩ ሞጋች ስለነበር ነው። ጽሑፎቹ የሕዝቡን እውነተኛ ሕይወት የሚዳስሱ እንዲሁም ችግሩንና በደሉን ከፍላጐቱ ጋር የሚያመለክቱ ነበሩ። በተለይም የሥርዓቱን ንቅዘት በመዋጋት የሚደርስበት አሳርና መከራ ከሙያው አላገደውም። መንግስቱ ‹‹የኢትዮጵያ ጋዜጠኞች የገና ዳቦ ናቸው›› ሲል ብዙ ጊዜ ተናግሯል።
መንግሥቱ የማተሚያ ቤት እዳ መክፈል ተስኖት ሲሰቃይ ቢሸጡ ኖሮ ከማተሚያ ቤቱ እዳ የሚበልጥ ገንዘብ ሊያወጡ የሚችሉ መጽሐፍቱን ለየድርጅቶቹ በነፃ ያድል እንዲሁም ለመጻሕፍት አዟሪዎችም በነፃና በዱቤ ይሰጥ ነበር። ስለአብዛኞቹ መጽሐፍቱ ይዘት ግን አያስታውስም ነበር፤ የመጽሐፍቱ ቅጂም ኖሮት አያውቅም ነበር ይባላል። ስለመንግሥቱ ገዳሙ ሲነሳ አብሮ የሚታወሰው አወዛጋቢና አስቂኝ ባህርያቱ እንዲሁም በፈተና የተሞላው የሕይወት ጉዞው ናቸው። የመንግሥቱ ሕይወት በሙሉ ውጣ ውረድ የበዛበት ነበር። የሚሰራቸው ነገሮች አብዛኞቹ የሚያስደምሙና የሚያስቁ ነበሩ። ከላይ ከተጠቀሱት አለቆቹን የማስፈራራትና የመናቅ ድርጊቶቹ በተጨማሪ ሌሎች አስገራሚ ባህርያቱንና ድርጊቶቹን በጥቂቱ እንመልከት።
በአንድ ወቅት ለስራ ጉዳይ ወደ አስመራ ይላካል። ታዲያ በየፖሊስ ጣቢያው ስለሚገኙት ማረሚያ ቤቶች ሁኔታ መጻፍ ፈለገ። ባለስልጣኑን ለማስፈቀድ ቢሞክርም ሳይሳካለት ቀረ። ሞገደኛው መንግሥቱ ግን ወንጀል ሰርቶ ፖሊስ ጣቢያ መግባትን ለዓላማው ማሳኪያ አድርጎ ሊጠቀምበት አሰበ። ወደ አንድ መጠጥ ቤት ጎራ ይልና ባዶ ጠርሙሶችን እየመረጠ መሰባበር ጀመረ።
ኡኡታው ቀለጠና ፖሊስ እያዳፋ ወደ ፖሊስ ጣቢያ ወሰደው። ከሦስት ቀናት በኋላ በዋስ ተለቆ አዲስ አበባ ሲመለስ ስለአስመራ ፖሊስ ጣቢያዎች በርከት ያሉ መጣጥፎችን መፃፍ ቻለ። የአዲስ አበባን ፖሊስ ጣቢያዎች ለመጎብኘት ስላቀደ ሌላ አምባጓሮ ፈጥሮ ፖሊስ ጣቢያዎቹን በእስረኛነት ጎብኝቷቸዋል።
መንግሥቱ አንዱን ምስኪን ፈረንጅ በ700 ብር ደመወዝ ቀጥሮ ካፖርት እያሸከመ በፒያሳ ይዞር ነበር። ይህም ‹‹ፈረንጅ የሐበሻ አሽከር አይሆንም›› የሚለው አመለካከት ስህተት መሆኑን በተግባር ለማሳየት ነበር።
4 ኪሎ አካባቢ አንድ ተወዳጅ ውስኪ ቤት ነበር። ታዲያ የውስኪ ወዳጆች ቤቱን ከአፍ እስከገደፉ ድረስ እየሞሉት መቀመጫ አይገኝም ነበር። አንድ ቀን መንግሥቱ ከአንድ የውጭ ጋዜጠኛ ጋር ውስኪ ለመጠጣት ወደ ውስኪ ቤቱ ሲሄድ እንኳን መቀመጫ መቆሚያም ይጠፋል። መንግሥቱ በሩ ላይ ቆሞ አጨበጨበ።
ጠጪው ሁሉ ፀጥ ሲል በወቅቱ የነበሩትን ጠቅላይ ሚኒስትር አክሊሉ ሀብተወልድን ጨምሮ ብዙ የመንግሥት ሹማምንትን ስም እያነሳ መሳደብ ጀመረ። ምድረ ጠጪም ‹‹የመንግሥቱ ስድብ ያሳፍሰናል›› በሚል ስጋት ሂሳቡን እየከፈለ ቤቱን ለቆ ወጣ። ቤቱ ጭር ሲል መንግሥቱ ከወዳጁ ጋር ምቹ ሶፋ ላይ ተቀምጦ ውስኪን መጠጣት ጀመረ።
መንግስቱ ገዳሙ አንጋፋ ጠጪ በመባል የሚታወቅ ሲሆን ለምን እንደሚጠጣ ሲጠየቅ፤ ‹‹እኔ እኮ ለምን እንደምጠጣ እናንተ ደንቆሮዎች ስለሆናችሁ አይገባችሁም፤ የእኔ አእምሮ ከተራው ሰው አእምሮ በጣም የላቀ ነው። ስለዚህ ከእናንተ ጋር ለመነጋገር ያንን ከፍተኛ አእምሮዬን ወደ እናንተ ደረጃ ላወርደው የምችለው በአልኮል ኃይል ነው›› በማለት መናገሩ ይታወሳል።
መንግሥቱ ከጽሑፉና ከንግግሩ ባሻገር በእለታዊ ድርጊቱ ሁሉ ሥርዓቱን ይቃወም ነበር። አንዲት አህያ ጆሮዋ ላይ ብር ለጥፎ በየመጠጥ ቤቱ እየዞረ፣ አስተናጋጆቹ እንዲታዘዟት ያደርግ ነበር። በዚህም የጊዜው ባለስልጣኖች በገንዘብ እንጂ በአስተሳሰብ ከአህያ እንደማይሻሉ ለማስረዳት ያደረገው ነው ተብሏል።
አህያዋን ይዟት በየቦታው ሲዞር ‹‹ምንድን ነች?›› ብለው ሲጠይቁትም ‹‹የማስታወቂያ ሚኒስቴር ባልደረባ ነች›› እያለ ይመልስ እንደነበር ይወሳል፤ በዚያ ዘመን ማስታወቂያውን በአህያ እየዞረ የሚያስነግረው ብሔራዊ ሎተሪ፤ በማስታወቂያ ሚኒስቴር ሥር ነበር። በመንግሥቱ እሳቤ አህያዋ የባለስልጣኖች ተምሳሌት ነበረች። የ 1953 ዓ.ም የመፈንቅለ መንግሥት ሙከራን ደግፎ ሕዝቡን መቀስቀሱም ስርዓቱን የመቃወሙ ምልክት ነበር።
በሌላ ጊዜ ደግሞ በመስሪያ ቤቱ ግብዣ ላይ የአለቃው አለቃ ባለመገኘታቸው ይወርፋቸዋል። ድርጊቱ ‹‹ክብረ ነክ›› ተብሎ በማግሥቱ ኮሚቴ ተቋቁሞ ለፍርድ ቀረበ። ጥፋቱን የፈጸመበትን ምክንያት እንዲያብራራ ሲጠየቅ ‹‹ሰዎች ገፋፍተውኝ ነው›› ብሎ መለሰ።
እነማን እንደሆኑ ሲጠየቅም ለፍርድ የተሰየሙትን አባላት ስም ጠቀሰ። በዚህ የተነሳ የኮሚቴው አባላት ዳኝነቱን ትተው መንግሥቱን ለመደብደብ ከጀሉ። መንግሥቱ ሮጦ ወጣ፤ የተናደዱት የኮሚቴው አባላት ግን ተከትለው ያባር ሩታል። መንግሥቱ የኮሚቴው አባላት ስሜታቸውን መቆጣጠር የሚችሉ አለመሆናቸውን በአደባባይ አሳየ።
ሌላ ጊዜ ደግሞ መንግሥቱን ሮም ከተማን እንዲጎበኝ ተጋበዘ። መንጌ ትኬቱን፣ ፓስፖርቱንና ቪዛውን በእጁ ካስገባ በኋላ በበረራው ዋዜማ ቀን ወደ አለቃው ዘንድ ሄዶ ከሳምንት በኋላ ወደ አውሮፓ እንደሚሄድና ጉዞውን እንዲፈቅዱለትም አንጀት የሚበላ ደብዳቤ ፅፎ ሰጣቸው።
አለቃውም የሚያስቸግራቸው ሰራተኛቸው በእጃቸው ላይ መውደቁ አስደስቷቸው ‹‹ደብዳቤው ከማኅደሩ ጋር ተያይዞ ይቀመጥ›› የሚል ትዕዛዝ ጽፈው ማመልከቻውን ወደ መዝገብ ቤት ላኩት። መንግሥቱ እንደተጫወተባቸው አለቃው ያወቁት ጠዋት ለስራ ሲፈልጉት በዚያው ቀን ጠዋት ቀደም ብሎ ወደ ሮም መብረሩ ሲነገራቸው ነበር።
ሌላኛው የመንግሥቱ ጠባይ አምባጓሮ መውደዱ ነበር። በዚህም ጠባዩ ምክንያት ከመቶ ጊዜ በላይ ተቧቅሷል። አራት ጊዜ በጩቤ ተወግቷል፤ አራት ጊዜ በመኪና ተገጭቷል፤ ህሊናውን እስከሚስት ድረስ ያጋ ጠመውን ጨምሮ 20 ጊዜ ማጅራቱን በወሮበላዎች ተመትቷል። አንድ ሙሉ ሌሊት በቆሻሻ ክምር ላይ አሳልፏል።
አንድ መ/ቤት እየሰራ እያለ አለቃው ዕድገት አግኝተው ወደ ሌላ ቦታ ሲሄዱ የሽኝት ፕሮግራም ይዘጋጅላቸዋል። ለፕሮግራሙ ከሁሉም ሰራተኞች የበለጠ መዋጮ አዋጣ። "ለምን ይሆን ይሄን ያደረከው?" ተብሎ ሲጠየቅ "አለቃዬ እዚህ እንዳይቀር ብሎም ወደዚህ ተመልሶ እንዳይመጣ ነው።" በማለት አስገራሚ መልስ ሰጥቷል።
መንግሥቱ በራሱ ላይ መቀለድም ይወድ ነበር። አንድ ጊዜ ሳይሞት ‹‹ሞቻለሁ›› ብሎ በሌላ ሰው በኩል በማስነገር ወደ መስሪያ ቤቱ ስልክ አስደውሎ የቀብሩ ቦታ ቀጨኔ መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን እንደሆነ አሳወቀ። ለቀስተኛው በቤተ-ክርስቲያኑ ተገኝቶ ተሰብስቦ አስከሬን ሲጠብቅ መንግሥቱ ጥቁር ሱፉን ግጥም አድርጎና ባርኔጣውን ደፍቶ ብቅ አለ። ለቀስተኛውን አመስግኖ ሳይሞት ‹‹ሞቻለሁ›› ብሎ ያስነገረው በእውነት ቢሞት የቀብሩ ስነ ስርዓት ምን እንደ ሚመስል በቁሙ ለማየት ፈልጎ ያደረገው መሆኑን ገለፆ ለቀስተኛውን በተነ።
መንግሥቱ በዓለም ዙሪያ ታዋቂ ሰዎችን በሚመዘግበው የ‹‹Who is Who›› ባሕረ መዝገብ ውስጥ ስሙ ሰፍሮለታል። ‹‹ትዳርን ለምርምር የሚጠቀምበት ይመስላል›› እስከሚባል ድረስ አራት ጊዜ አግብቶ አራት ጊዜ ፈትቷል።
መንግስቱ ሊሞት አንድ ሳምንት ሲቀረው "መንግስቱ ገዳሙ ሰሞኑን ይሞታል" እያለ በራሱ ላይ አሟርቶ በተወለደ በ48 ዓመቱ በተናገረው ሳምንቱ ውስጥ ሐምሌ 29 ቀን 1977 ዓ/ም ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል።
ከስራዎቹ መካከልም፡-
-- አመፀኛ ሞግዚት -- እንኮዬ ደማሜ
-- ብታምንም ባታምንም -- ኮሳሳው ተማሪ
-- የእንስሳት ሮኬት -- ፃድቁ አራምዴ
-- ማጅራት መቺ -- አሳማና ድመት
-- ከምሱር -- አንተ ማን ነህ
-- የሃምሳ አለቃ ገብሬ -- አመሰግንሻለሁ
-- The Psychology of The White Races
-- የአልማዝ እዳ
-- ከማን አንሼ .....… የሚሉት ይጠቀሳሉ።
አዲስ ዘመን (መጋቢት 22 ቀን 2013)
ተጨማሪ የተለያዩ ማኅበራዊ ገጾች
Via #ሙክታሮቪች
#getutemesgen #getu #ጌጡ
3 months ago
አደገኛው እጽ አዘዋወሬ “ኤል ሜንቾ” በወርቅ ሳጥን ተቀበረ
#ethiopia | ለዓመታት በዓለም አቀፍ ደረጃ ሲፈለግ የነበረውና የአሜሪካ መንግሥት ለጭንቅላቱ 15 ሚሊዮን ዶላር መድቦለት የነበረው የጃሊስኮ ኒው ጄነሬሽን ካርቴል (CJNG) መሪ ኔሜሲዮ ኦሴጌራ ሰርቫንቴስ (ኤል ሜንቾ)፣ ከሜክሲኮ ልዩ ኃይሎች ጋር በነበረ የተኩስ ልውውጥ መገደሉ ተረጋግጧል። በታፓልፓ በተካሄደ ወታደራዊ ዘመቻ በደረሰበት ቁስል ሕይወቱ ያለፈው የ59 ዓመቱ ኤል ሜንቾ፣ የቀብር ሥነ-ሥርዓቱ በጓዳላሃራ ከተማ በከፍተኛ ድምቀትና ጥበቃ ተከናውኗል።
በወርቅ ሳጥን የታጀበ ሽኝት
የዚህ አደገኛ ወንጀለኛ ቀብር በብዙዎች ዘንድ መነጋገሪያ የሆነው እንደ መጨረሻ ፍላጎቱ በተዘጋጀለት ውድ የወርቅ የሬሳ ሳጥን ምክንያት ነው። ይህ የቅንጦት ቀብር በሕይወት እያለ ያከማቸውን ግዙፍ ሀብትና የነበረውን ስልጣን ማሳያ ተደርጎ ተወስዷል። የቀብር ሂደቱ ባህላዊ የሜክሲኮ ሙዚቃዎች (Banda) እየተሰሙና ፊታቸውን በሸፈኑ የካርቴል አባላት ታጅቦ ተፈጽሟል።
ከሞቱ በኋላ የቀጠለው ትርምስ
የኤል ሜንቾ መገደል በሜክሲኮ ሰላምን ከማምጣት ይልቅ አዲስ የግርግር ምዕራፍ ከፍቷል፦
* የሕይወት መጥፋት፦ በ20 የሜክሲኮ ግዛቶች ውስጥ በተቀሰቀሰ ግጭት እስካሁን የ70 ሰዎች ሕይወት አልፏል።
* የበቀል እርምጃ፦ የካርቴሉ አባላት አውራ ጎዳናዎችን በመዝጋትና ተሽከርካሪዎችን በማቃጠል መንግሥትን እየተፈታተኑ ይገኛሉ።
* የስልጣን ሽኩቻ፦ የመሪውን መሞት ተከትሎ በቡድኑ ውስጥ በሚፈጠር የስልጣን ሹክቻ የሀገሪቱ የፀጥታ ሁኔታ ይበልጥ ስጋት ላይ ወድቋል።
ምንም እንኳን የሜክሲኮ መንግሥት ግድያውን እንደ ትልቅ ድል ቢቆጥረውም፣ “ሀብትና ስልጣን እስከ መቃብር ይከተላሉን?” የሚለው ጥያቄና በሀገሪቱ የነገሠው አለመረጋጋት የብዙዎችን ትኩረት ስቧል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #ኤል_ሜንቾ #ሜክሲኮ #ካርቴል #ወንጀል #ዓለም_አቀፍ_ዜና #elmencho #mexico #cjng #breakingnews
#ethiopia | ለዓመታት በዓለም አቀፍ ደረጃ ሲፈለግ የነበረውና የአሜሪካ መንግሥት ለጭንቅላቱ 15 ሚሊዮን ዶላር መድቦለት የነበረው የጃሊስኮ ኒው ጄነሬሽን ካርቴል (CJNG) መሪ ኔሜሲዮ ኦሴጌራ ሰርቫንቴስ (ኤል ሜንቾ)፣ ከሜክሲኮ ልዩ ኃይሎች ጋር በነበረ የተኩስ ልውውጥ መገደሉ ተረጋግጧል። በታፓልፓ በተካሄደ ወታደራዊ ዘመቻ በደረሰበት ቁስል ሕይወቱ ያለፈው የ59 ዓመቱ ኤል ሜንቾ፣ የቀብር ሥነ-ሥርዓቱ በጓዳላሃራ ከተማ በከፍተኛ ድምቀትና ጥበቃ ተከናውኗል።
በወርቅ ሳጥን የታጀበ ሽኝት
የዚህ አደገኛ ወንጀለኛ ቀብር በብዙዎች ዘንድ መነጋገሪያ የሆነው እንደ መጨረሻ ፍላጎቱ በተዘጋጀለት ውድ የወርቅ የሬሳ ሳጥን ምክንያት ነው። ይህ የቅንጦት ቀብር በሕይወት እያለ ያከማቸውን ግዙፍ ሀብትና የነበረውን ስልጣን ማሳያ ተደርጎ ተወስዷል። የቀብር ሂደቱ ባህላዊ የሜክሲኮ ሙዚቃዎች (Banda) እየተሰሙና ፊታቸውን በሸፈኑ የካርቴል አባላት ታጅቦ ተፈጽሟል።
ከሞቱ በኋላ የቀጠለው ትርምስ
የኤል ሜንቾ መገደል በሜክሲኮ ሰላምን ከማምጣት ይልቅ አዲስ የግርግር ምዕራፍ ከፍቷል፦
* የሕይወት መጥፋት፦ በ20 የሜክሲኮ ግዛቶች ውስጥ በተቀሰቀሰ ግጭት እስካሁን የ70 ሰዎች ሕይወት አልፏል።
* የበቀል እርምጃ፦ የካርቴሉ አባላት አውራ ጎዳናዎችን በመዝጋትና ተሽከርካሪዎችን በማቃጠል መንግሥትን እየተፈታተኑ ይገኛሉ።
* የስልጣን ሽኩቻ፦ የመሪውን መሞት ተከትሎ በቡድኑ ውስጥ በሚፈጠር የስልጣን ሹክቻ የሀገሪቱ የፀጥታ ሁኔታ ይበልጥ ስጋት ላይ ወድቋል።
ምንም እንኳን የሜክሲኮ መንግሥት ግድያውን እንደ ትልቅ ድል ቢቆጥረውም፣ “ሀብትና ስልጣን እስከ መቃብር ይከተላሉን?” የሚለው ጥያቄና በሀገሪቱ የነገሠው አለመረጋጋት የብዙዎችን ትኩረት ስቧል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #ኤል_ሜንቾ #ሜክሲኮ #ካርቴል #ወንጀል #ዓለም_አቀፍ_ዜና #elmencho #mexico #cjng #breakingnews
4 months ago
የአቶ አማን ፍስሃጽዮን አስከሬን አዲስ አበባ ገባ፤ የሽኝት መርሃ ግብር ነገ ይከናወናል
#fastmereja I የኢቢኤስ (EBS) ቴሌቪዥን መስራችና ዋና ስራ አስፈጻሚ የነበሩት የአቶ አማን ፍስሃጽዮን አስከሬን ዛሬ ማለዳ አዲስ አበባ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ደርሷል።
በአየር ማረፊያው ለታዋቂው የሜዲያ ሰው የክብር አቀባበል የተደረገ ሲሆን፣ ቤተሰቦቻቸው፣ ወዳጅ ዘመዶቻቸውና የስራ ባልደረቦቻቸው በተገኙበት በታላቅ ስነ-ስርዓት ታጅበው ሳር ቤት አካባቢ ወደሚገኘው መኖሪያ ቤታቸው አምርተዋል።
የነገው የሽኝት መርሃ ግብር
ለአቶ አማን ፍስሃጽዮን የሚደረገው የስንብት መርሃ ግብር ነገ የካቲት 12 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ አድዋ ሙዚየም እንደሚከናወን ታውቋል።
• ከጠዋቱ 3:00 ሰዓት፦ አስከሬኑ ከመኖሪያ ቤታቸው ተነስቶ ወደ አድዋ ሙዚየም ጉዞ ይደረጋል።
• ቦታ፦ አድዋ ሙዚየም (የመጨረሻ የሽኝት መርሃ ግብር)።
#fastmereja I የኢቢኤስ (EBS) ቴሌቪዥን መስራችና ዋና ስራ አስፈጻሚ የነበሩት የአቶ አማን ፍስሃጽዮን አስከሬን ዛሬ ማለዳ አዲስ አበባ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ደርሷል።
በአየር ማረፊያው ለታዋቂው የሜዲያ ሰው የክብር አቀባበል የተደረገ ሲሆን፣ ቤተሰቦቻቸው፣ ወዳጅ ዘመዶቻቸውና የስራ ባልደረቦቻቸው በተገኙበት በታላቅ ስነ-ስርዓት ታጅበው ሳር ቤት አካባቢ ወደሚገኘው መኖሪያ ቤታቸው አምርተዋል።
የነገው የሽኝት መርሃ ግብር
ለአቶ አማን ፍስሃጽዮን የሚደረገው የስንብት መርሃ ግብር ነገ የካቲት 12 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ አድዋ ሙዚየም እንደሚከናወን ታውቋል።
• ከጠዋቱ 3:00 ሰዓት፦ አስከሬኑ ከመኖሪያ ቤታቸው ተነስቶ ወደ አድዋ ሙዚየም ጉዞ ይደረጋል።
• ቦታ፦ አድዋ ሙዚየም (የመጨረሻ የሽኝት መርሃ ግብር)።
4 months ago
💔 የአቶ አማን ፍስሃጽዮን አስከሬን አዲስ አበባ ገባ፤
ነገ የስንብት መርሃ ግብር ይከናወናል 🕯️
#ethiopia | የኢቢኤስ (EBS) ቴሌቪዥን መስራችና ዋና ስራ አስፈጻሚ የነበሩት ታዋቂው ባለሙያ የአቶ አማን ፍስሃጽዮን አስከሬን ዛሬ ማለዳ አዲስ አበባ ቦሌ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ ደርሷል።
በአየር ማረፊያውም የክብር አቀባበል ተደርጎለታል።
አስከሬኑ በቤተሰቦች፣ በወዳጅ ዘመዶችና በስራ ባልደረቦች ታጅቦ ሳር ቤት አካባቢ ወደሚገኘው መኖሪያ ቤታቸው ደርሷል።
የነገው የክብር ስንብት መርሃ ግብር፦
📅 ነገ ሐሙስ የካቲት 12 ቀን 2018 ዓ.ም.
🕒 ከጠዋቱ 3፡00 ሰዓት ጀምሮ ከመኖሪያ ቤታቸው ወደ አድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም ጉዞ ይደረጋል።
📍 ስነ-ስርዓት፦
በአድዋ ሙዚየም አዳራሽ ልዩ የሽኝትና የስንብት መርሃ ግብር ይከናወናል።
አቶ አማን በኢትዮጵያ የሚዲያ ታሪክ ውስጥ ዘመናዊና ጥራት ያለው የቴሌቪዥን ስርጭት እንዲኖር ካደረጉ ቀዳሚ ባለሙያዎች አንዱ ነበሩ።
ለቤተሰቦቻቸው፣ ለወዳጅ ዘመዶቻቸውና ለኢቢኤስ ቴሌቪዥን ሰራተኞች በሙሉ መጽናናትን እንመኛለን።
ፈጣሪ ነፍሳቸውን በአጸደ ገነት ያኑርልን። 🙏🕯️
#amanfissehazion #ebs #ebsworldwide #ethiopia #medialegend #restinpeace #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን
ነገ የስንብት መርሃ ግብር ይከናወናል 🕯️
#ethiopia | የኢቢኤስ (EBS) ቴሌቪዥን መስራችና ዋና ስራ አስፈጻሚ የነበሩት ታዋቂው ባለሙያ የአቶ አማን ፍስሃጽዮን አስከሬን ዛሬ ማለዳ አዲስ አበባ ቦሌ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ ደርሷል።
በአየር ማረፊያውም የክብር አቀባበል ተደርጎለታል።
አስከሬኑ በቤተሰቦች፣ በወዳጅ ዘመዶችና በስራ ባልደረቦች ታጅቦ ሳር ቤት አካባቢ ወደሚገኘው መኖሪያ ቤታቸው ደርሷል።
የነገው የክብር ስንብት መርሃ ግብር፦
📅 ነገ ሐሙስ የካቲት 12 ቀን 2018 ዓ.ም.
🕒 ከጠዋቱ 3፡00 ሰዓት ጀምሮ ከመኖሪያ ቤታቸው ወደ አድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም ጉዞ ይደረጋል።
📍 ስነ-ስርዓት፦
በአድዋ ሙዚየም አዳራሽ ልዩ የሽኝትና የስንብት መርሃ ግብር ይከናወናል።
አቶ አማን በኢትዮጵያ የሚዲያ ታሪክ ውስጥ ዘመናዊና ጥራት ያለው የቴሌቪዥን ስርጭት እንዲኖር ካደረጉ ቀዳሚ ባለሙያዎች አንዱ ነበሩ።
ለቤተሰቦቻቸው፣ ለወዳጅ ዘመዶቻቸውና ለኢቢኤስ ቴሌቪዥን ሰራተኞች በሙሉ መጽናናትን እንመኛለን።
ፈጣሪ ነፍሳቸውን በአጸደ ገነት ያኑርልን። 🙏🕯️
#amanfissehazion #ebs #ebsworldwide #ethiopia #medialegend #restinpeace #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን
4 months ago
🕯️ የአቶ አማን ፍሰሃፂዮን የክብር ሽኝት እና የሥንብት መርሃ ግብር 🕯️
#ethiopia | የአቶ አማን ፍሰሃፂዮን አስከሬን አቀባበል፣ የክብር ስንብት እና የቀብር አስፈጻሚ ኮሚቴ፤ የቀብር ስነ-ስርዓቱን አስመልክቶ የሚከተለውን መርሃ ግብር አውጥቷል።
📅 የሥንብት ቀን፦ ሐሙስ የካቲት 12 ቀን 2018 ዓ.ም.
📍 የስንብት ቦታ፦ አድዋ ሙዚየም
የመውጫ ሰዓታት ዝርዝር፦
🕒 3፡00 ሰዓት፦
ጉዞ ከመኖሪያ ቤታቸው ወደ አድዋ ሙዚየም ይጀመራል።
🕒 5፡00 ሰዓት፦
ለአጭር የሥንብት መርሃ ግብር አስከሬኑ አድዋ ሙዚየም ይደርሳል።
🕒 8፡00 ሰዓት፦
አስከሬኑ ከሙዚየሙ ወደ መጨረሻ ማረፊያው ጉዞ ይጀምራል።
🕒 9፡00 ሰዓት፦
በጴጥሮስ ወጳውሎስ መካነ መቃብር የግብዓተ መሬት ስነ-ስርዓት ይፈጸማል።
የአቶ አማን ፍሰሃፂዮን የክብር ሽኝት ከላይ በተገለጸው መሠረት የሚፈጸም መሆኑን ከባለቤቱ፣ ከልጆቹ፣ ከቤተሰቦቻቸው እና ከቀብር አስፈፃሚ ኮሚቴው የተላለፈ መልዕክት ነው።
ለቤተሰቦቻቸውና ለወዳጆቻቸው መጽናናትን እንመኛለን።
#amanfisehatsion #ethiopia #addisababa #adwamuseum #remembrance #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን
#ethiopia | የአቶ አማን ፍሰሃፂዮን አስከሬን አቀባበል፣ የክብር ስንብት እና የቀብር አስፈጻሚ ኮሚቴ፤ የቀብር ስነ-ስርዓቱን አስመልክቶ የሚከተለውን መርሃ ግብር አውጥቷል።
📅 የሥንብት ቀን፦ ሐሙስ የካቲት 12 ቀን 2018 ዓ.ም.
📍 የስንብት ቦታ፦ አድዋ ሙዚየም
የመውጫ ሰዓታት ዝርዝር፦
🕒 3፡00 ሰዓት፦
ጉዞ ከመኖሪያ ቤታቸው ወደ አድዋ ሙዚየም ይጀመራል።
🕒 5፡00 ሰዓት፦
ለአጭር የሥንብት መርሃ ግብር አስከሬኑ አድዋ ሙዚየም ይደርሳል።
🕒 8፡00 ሰዓት፦
አስከሬኑ ከሙዚየሙ ወደ መጨረሻ ማረፊያው ጉዞ ይጀምራል።
🕒 9፡00 ሰዓት፦
በጴጥሮስ ወጳውሎስ መካነ መቃብር የግብዓተ መሬት ስነ-ስርዓት ይፈጸማል።
የአቶ አማን ፍሰሃፂዮን የክብር ሽኝት ከላይ በተገለጸው መሠረት የሚፈጸም መሆኑን ከባለቤቱ፣ ከልጆቹ፣ ከቤተሰቦቻቸው እና ከቀብር አስፈፃሚ ኮሚቴው የተላለፈ መልዕክት ነው።
ለቤተሰቦቻቸውና ለወዳጆቻቸው መጽናናትን እንመኛለን።
#amanfisehatsion #ethiopia #addisababa #adwamuseum #remembrance #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን
Sponsored by
Surafel
4 months ago
⚫️ የጽናት እና የአብሮነት ተምሳሌቱ መቶ አለቃ ለማ አስፋው አረፉ 🕯️🇪🇹
#ethiopia | ከአየር ኃይል መኮንንነት እስከ አለማ ፋርምስ ስኬት... የብርቱው ባለሙያ እና የቅን ሰው ሽኝት
በሀገራችን የግብርና ቢዝነስ (Agribusiness) ውስጥ ስመ ጥር የሆነው የ"አለማ ፋርምስ" መስራች አባል የነበሩት መቶ አለቃ ለማ አስፋው ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል።
መቶ አለቃ ለማ እና ጓደኛቸው ሻለቃ አለማየሁ አምደማርያም ከአየር ኃይል ተሰናብተው በችግር ውስጥ በነበሩበት ወቅት፤ እጃቸውን ለልመና ሳይዘረጉ በዶሮ እርባታ የጀመሩት ጉዞ ዛሬ ግዙፍ ተቋም ሆኖ ቆሟል።
ለምን ይዘከራሉ?
የጽናት ምሳሌ፦
ወታደራዊ ማዕረጋቸው ሳይገግዳቸው በጓሮ አትክልት እና በዶሮ እርባታ ስራን የጀመሩ፣ "ሰው በላቡ ይኑር" የሚለውን መርህ በተግባር ያሳዩ ብርቱ ሰው ነበሩ።
የአብሮነት ተምሳሌት፦
ከሻለቃ አለማየሁ ጋር ለረጅም ዓመታት በአንድነት፣ በመከባበር እና በመግባባት የገነቡት ተቋም ለሀገራችን የቢዝነስ ዘርፍ ብርቅ የሆነ "የጋራ ስኬት" አርአያ ነው።
ሰብአዊነት እና ቅንነት፦
የቅርብ ወዳጆቻቸው እንደሚመሰክሩት፤ መቶ አለቃ ለማ ሁሉን አክባሪ፣ ሳቂታ፣ ለሙያ አጋሮቹ እውቀቱን እና ቁሳቁሱን የማይሰስት ደግ ሰው ነበሩ።
በደብረዘይት (ቢሾፍቱ) ኪዳነ ምህረት ቤተ-ክርስቲያን የቀብር ሥነ-ሥርዓታቸው ተፈጽሟል።
ለቤተሰቦቻቸው፣ ለልብ ጓደኛቸው ለሻለቃ አለማየሁ እና ለወዳጅ ዘመዶቻቸው ሁሉ መጽናናትን እንመኛለን።
ፈጣሪ ነፍሳቸውን በገነት ያሳርፍ!
#lemaasfaw #alemafarms #ethiopianentrepreneur #successstory #bishoftu #inspiration #restinpeace #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን
#ethiopia | ከአየር ኃይል መኮንንነት እስከ አለማ ፋርምስ ስኬት... የብርቱው ባለሙያ እና የቅን ሰው ሽኝት
በሀገራችን የግብርና ቢዝነስ (Agribusiness) ውስጥ ስመ ጥር የሆነው የ"አለማ ፋርምስ" መስራች አባል የነበሩት መቶ አለቃ ለማ አስፋው ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል።
መቶ አለቃ ለማ እና ጓደኛቸው ሻለቃ አለማየሁ አምደማርያም ከአየር ኃይል ተሰናብተው በችግር ውስጥ በነበሩበት ወቅት፤ እጃቸውን ለልመና ሳይዘረጉ በዶሮ እርባታ የጀመሩት ጉዞ ዛሬ ግዙፍ ተቋም ሆኖ ቆሟል።
ለምን ይዘከራሉ?
የጽናት ምሳሌ፦
ወታደራዊ ማዕረጋቸው ሳይገግዳቸው በጓሮ አትክልት እና በዶሮ እርባታ ስራን የጀመሩ፣ "ሰው በላቡ ይኑር" የሚለውን መርህ በተግባር ያሳዩ ብርቱ ሰው ነበሩ።
የአብሮነት ተምሳሌት፦
ከሻለቃ አለማየሁ ጋር ለረጅም ዓመታት በአንድነት፣ በመከባበር እና በመግባባት የገነቡት ተቋም ለሀገራችን የቢዝነስ ዘርፍ ብርቅ የሆነ "የጋራ ስኬት" አርአያ ነው።
ሰብአዊነት እና ቅንነት፦
የቅርብ ወዳጆቻቸው እንደሚመሰክሩት፤ መቶ አለቃ ለማ ሁሉን አክባሪ፣ ሳቂታ፣ ለሙያ አጋሮቹ እውቀቱን እና ቁሳቁሱን የማይሰስት ደግ ሰው ነበሩ።
በደብረዘይት (ቢሾፍቱ) ኪዳነ ምህረት ቤተ-ክርስቲያን የቀብር ሥነ-ሥርዓታቸው ተፈጽሟል።
ለቤተሰቦቻቸው፣ ለልብ ጓደኛቸው ለሻለቃ አለማየሁ እና ለወዳጅ ዘመዶቻቸው ሁሉ መጽናናትን እንመኛለን።
ፈጣሪ ነፍሳቸውን በገነት ያሳርፍ!
#lemaasfaw #alemafarms #ethiopianentrepreneur #successstory #bishoftu #inspiration #restinpeace #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን
4 months ago
የራዕይ ሰው ስንብት፡ አማን ፍስሃጽዮን እና ያልተጨረሰው የዲጂታል ድልድይ
በአንድ ወቅት ታዋቂው ደራሲ ጋብርኤል ጋርሲያ ማርኬዝ "ሰው መሞት በሚገባው ጊዜ ሳይሆን መሞት በሚችልበት ጊዜ ነው የሚሞተው" ብሎ ነበር። ይህ አባባል ለአማን ፍስሃጽዮን እጅግ ይቀርባል። አማን መሞት የሚገባው ሰው አልነበረም፤ ገና ብዙ የሚያልማቸው ህልሞች፣ ሊገነባቸው ያሰባቸው የሚዲያ መንደሮችና ሊያሻግራቸው ያቀዳቸው ወጣቶች ነበሩ።
ነገር ግን በ 54 አመቱ፣ የካንሰር ህመም በደካማው ስጋው ላይ በርትቶበት፣ በስተመጨረሻ በሄደበት አሜሪካ በዝምታ አሸለበ። ይህ ፅሁፍ የአንድን ሰው ሞት ብቻ ሳይሆን፣ የአንድን ትልቅ ራዕይ ጊዜያዊ መቆም የሚተርክ ልብ አንጠልጣይ ስንብት ነው።
አማን ለሦስት ዓመታት ያህል ከካንሰር ጋር ሲታገል ቆይቷል። ህመሙ አንዴ ሻል እያለው ተስፋ ሲሰጠው፣ መልሶ ደግሞ ክፉኛ እያመመው ሲያሰቃየው ነበር። ህመም እንደ ውቅያኖስ ማዕበል ነው፤ ሲመጣ ሁሉንም ይዞ ይሄዳል፣ ሲመለስ ግን ባዶነትን ጥሎ ይከንፋል። አማን የመጨረሻው ሰዓት መቃረቡን በተረዳ ጊዜ፣ ለአንድ የቅርብ የሥራ ባልደረባው እንዲህ ብሎ ነበር፡- "የምድን አይመስለኝም... ኢትዮጵያ ውስጥ መሞት እፈልጋለሁ።" ይህ ቃል በሰው ልጅ ልብ ውስጥ ያለውን የትውልድ ሀገር ፍቅርና ናፍቆት ቁልጭ አድርጎ ያሳያል። "ባለፈው ሰኞ እመጣለሁ" ብሎ የገባው ቃል ግን፣ በአካላዊ ጉዞ ሳይሆን በነፍስ ሽኝት ተተካ።
የኢቢኤስ (EBS) ሰራተኞች አለቃቸው እንደማይመጣ አላሰቡም ነበር። ለእነሱ አማን ማለት የማይበገር ተራራ፣ በማንኛውም ማዕበል ውስጥ የማይናወጥ መሪ ነበር። አሜሪካ ለህክምና በተመላለሰ ቁጥር "ይመለሳል" የሚለው ተስፋቸው ፀንቶ ነበር። ቪክቶር ሁጎ "ሞት ማለት መጥፋት ሳይሆን ወደ ሌላ ክፍል መሸጋገር ነው" እንደሚለው ሁሉ፣ አማንም ወደ ሌላው ዓለም ሲሸጋገር በቢሮዎቹ ውስጥ የቀረው ባዶነት ግን የሚሞላ አልነበረም። ሰራተኞቹ ሰኞን የጠበቁት በአካል ሊቀበሉት እንጂ በሀዘን መግለጫ ሊሸኙት አልነበረም።
የአማን ታሪክ ሲነሳ የግዴታ ሌላውን የዓለም ክፍል ማስታወስ ይገባል። በ19ኛው ክፍለ ዘመን አሜሪካዊው የሚዲያ ንጉስ ጆሴፍ ፑሊትዘር ጋዜጠኝነትን ለህዝብ ቅርብ ለማድረግ የታገለው ትግል ከአማን ጋር ይመሳሰላል።
አማንም በ2008 በሜሪላንድ ሲልቨር ስፕሪንግ EBSን ሲመሰርት፣ ዓላማው ዳያስፖራውን ከሀገር ቤት ጋር ማገናኘት ብቻ አልነበረም፤ የኢትዮጵያን ሚዲያ ዘመናዊ ማድረግም እንጂ። ልክ እንደ ፑሊትዘር ሁሉ አማንም በስራው ላይ የሚሰነዘሩ ትችቶችን (መዝናኛ ብቻ ነው፣ ከውጭ የተቀዳ ነው የሚሉትን) በዝምታና በስራ ነበር የሚመልሰው። እሱ የሚያየው ከትችቱ ባሻገር ያለውን ትልቅ ምስል ነበር።
አማን ፍስሃጽዮን ሚዲያን እንደ ተራ መዝናኛ ሳይሆን እንደ "ኢንዱስትሪ" የተመለከተ ቀዳሚ ሰው ነው። በኢትዮጵያ አንድ ለእናቱ በነበረው ኢቲቪ (ETV) ዘመን፣ አማን የሳተላይት ቴሌቪዥን ባህልን ቀይሯል። ሰይፉ በኢቢኤስ፣ አስፋው፣ ነፃነት እና የጠፉ ቤተሰቦችን ፍለጋ ያሉ ፕሮግራሞች በኢትዮጵያውያን ሳሎን ውስጥ አዲስ ንፋስ ነፈሱ። እሱ በHD ጥራት ማሰራጨት ሲጀምር፣ ብዙዎች "ይህ ለኢትዮጵያ ገና ነው" ይሉ ነበር። እሱ ግን "ኢትዮጵያ ለጥራት ዝግጁ ነች" ብሎ ያምን ነበር። ጆርጅ በርናርድ ሾው "አንዳንዶች ነገሮችን ባሉበት ያዩና 'ለምን?' ይላሉ፤ እኔ ግን የሌሉ ነገሮችን አልምና 'ለምን አይሆንም?' እላለሁ" እንዳለው፣ አማንም "ለምን አይሆንም" ባይ ነበር።
በህይወቱ የመጨረሻ ቀናት አማን ስለ ሀገሩ ያለው ጭንቀት ከህመሙ በላይ ነበር። የኢትዮጵያ ቢዝነስ ሪቪው (EBR) እንደገለጸው፣ አማን የኢትዮጵያ ብሮድካስተሮች ማህበር ሰብሳቢ ሆኖ ሲያገለግል ለግል ሚዲያዎች ነፃነትና ዕድገት ተሟግቷል። የውጭ ምንዛሬ እጥረት፣ የሳተላይት ክፍያና የህግ ማዕቀፎች እንቅፋት ቢሆኑበትም፣ እሱ ግን ሁልጊዜም መፍትሄ አፈላላጊ ነበር። "ትዕግስት እና ጥራት" ለወጣቶች የሚሰጠው ትልቁ ምክሩ ነበር። ዛሬ ያ ምክሩ በኢቢኤስ ስቱዲዮዎች ውስጥ እንደ ማሚቶ ያስተጋባል።
አማን ላይ የሚሰነዘሩ ትችቶችም አልጠፉም ነበር። ፕሮግራሞቹ "ዐደንዛዥ" ናቸው፣ ወጣቱን አያነቁም የሚሉ ወገኖች ነበሩ። ነገር ግን አንድ የጥበብ ሰው "ትችት የማይሰነዘርበት ስራ፣ ስራ አይደለም" ይላል። አማን የሰዎችን ቤት በሳቅና በደስታ መሙላቱ፣ የጠፉ ቤተሰቦችን ማገናኘቱና ለብዙ ሺህ ወጣቶች የሥራ ዕድል መፍጠሩ የሚካድ ሀቅ አይደለም። የእሱ ህልም ኢትዮጵያውያን የራሳቸውን ታሪክ በራሳቸው አንደበት እንዲነግሩ ማስቻል ነበር። ይህ ራዕይ ደግሞ ከትችቶች ሁሉ በላይ ግዙፍ ነው።
የካቲት 4 ቀን 2018 ዓ.ም. የኢቢኤስ ማኔጅመንት የአማንን ህልፈት ሲያበስር መላው የሚዲያ ቤተሰብ ደንግጧል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ በሰጡት መግለጫ "አማን ለኢትዮጵያ የግል ሚዲያ ዕድገት ወሳኝ ሚና ከነበራቸው አንዱ ነው" ብለዋል። ይህ ምስክርነት አማን በህይወት ዘመኑ የዘራው ፍሬ ምን ያህል ጥልቅ እንደነበረ ያሳያል። እርግጥ ነው፣ አካሉ በአሜሪካ ቢረግፍም፣ አሻራው ግን በአዲስ አበባ ጎዳናዎችና በኢትዮጵያውያን ልብ ውስጥ ለዘላለም ይኖራል።
በአሁኑ ሰዓት በአሜሪካ ሜሪላንድ ግዛት የሽኝት መርሃ ግብሮች እየተከናወኑ ይገኛሉ። ዛሬ ሐሙስ እና ነገ ዓርብ በታኮማ ፓርክ ወዳጅ ዘመዶቹ ይሰበሰባሉ። ቅዳሜ ደግሞ በጸሎት ይሸኛል። ሁሉም ሰው የሚያወራው ስለ አማን ደግነት፣ ስለ ራዕዩና ስለ ብርቱነቱ ነው። አንቶን ቼኮቭ "ሰው ህያው የሚሆነው በሌሎች ትውስታ ውስጥ እስከኖረ ድረስ ነው" ይላል። አማን በፈጠረው የቴሌቪዥን ጣቢያና በለወጠው የሚዲያ ታሪክ ውስጥ ለዘላለም ህያው ሆኖ ይኖራል።
የቀብር አስፈፃሚ ኮሚቴው አስከሬኑ ወደ ኢትዮጵያ የሚመጣበትን ቀን እያመቻቸ ነው። አማን የተመኘው በሀገሩ አፈር ውስጥ ለማረፍ ነበር። ያ ምኞቱ ሊፈጸም ጥቂት ቀናት ቀርተውታል። የኢቢኤስ ስቱዲዮዎች ዛሬ ባዶ ቢመስሉም፣ የአማን መንፈስ ግን እዚያው አለ። "ራዕዩ ይቀጥላል" ያለው የጣቢያው መግለጫ፣ የአማን ሞት ፍፃሜ ሳይሆን የአዲስ ምዕራፍ ጅምር መሆኑን ያመለክታል።
በመጨረሻም፣ አማን ፍስሃጽዮን 54 ዓመታትን ብቻ አይደለም የኖረው፤ በሚሊዮኖች ልብ ውስጥ የሚቀመጡ በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዓታትን የሚዲያ ታሪክ ነው የሰራው። ከካንሰር ጋር ያደረገው ትግል በአካል ቢሸነፍም፣ በስራውና በታሪኩ ግን አሸናፊ ሆኖ አልፏል። "ኢትዮጵያ መሞት እፈልጋለሁ" ያለው ቃሉ፣ ለሀገሩ ያለውን የከበረ ፍቅር የመጨረሻ መግለጫ ሆኖ ይኖራል። ነፍስ ይማር አማን፤ ስራህ ግን ለዘላለም አይሞትም።
በአንድ ወቅት ታዋቂው ደራሲ ጋብርኤል ጋርሲያ ማርኬዝ "ሰው መሞት በሚገባው ጊዜ ሳይሆን መሞት በሚችልበት ጊዜ ነው የሚሞተው" ብሎ ነበር። ይህ አባባል ለአማን ፍስሃጽዮን እጅግ ይቀርባል። አማን መሞት የሚገባው ሰው አልነበረም፤ ገና ብዙ የሚያልማቸው ህልሞች፣ ሊገነባቸው ያሰባቸው የሚዲያ መንደሮችና ሊያሻግራቸው ያቀዳቸው ወጣቶች ነበሩ።
ነገር ግን በ 54 አመቱ፣ የካንሰር ህመም በደካማው ስጋው ላይ በርትቶበት፣ በስተመጨረሻ በሄደበት አሜሪካ በዝምታ አሸለበ። ይህ ፅሁፍ የአንድን ሰው ሞት ብቻ ሳይሆን፣ የአንድን ትልቅ ራዕይ ጊዜያዊ መቆም የሚተርክ ልብ አንጠልጣይ ስንብት ነው።
አማን ለሦስት ዓመታት ያህል ከካንሰር ጋር ሲታገል ቆይቷል። ህመሙ አንዴ ሻል እያለው ተስፋ ሲሰጠው፣ መልሶ ደግሞ ክፉኛ እያመመው ሲያሰቃየው ነበር። ህመም እንደ ውቅያኖስ ማዕበል ነው፤ ሲመጣ ሁሉንም ይዞ ይሄዳል፣ ሲመለስ ግን ባዶነትን ጥሎ ይከንፋል። አማን የመጨረሻው ሰዓት መቃረቡን በተረዳ ጊዜ፣ ለአንድ የቅርብ የሥራ ባልደረባው እንዲህ ብሎ ነበር፡- "የምድን አይመስለኝም... ኢትዮጵያ ውስጥ መሞት እፈልጋለሁ።" ይህ ቃል በሰው ልጅ ልብ ውስጥ ያለውን የትውልድ ሀገር ፍቅርና ናፍቆት ቁልጭ አድርጎ ያሳያል። "ባለፈው ሰኞ እመጣለሁ" ብሎ የገባው ቃል ግን፣ በአካላዊ ጉዞ ሳይሆን በነፍስ ሽኝት ተተካ።
የኢቢኤስ (EBS) ሰራተኞች አለቃቸው እንደማይመጣ አላሰቡም ነበር። ለእነሱ አማን ማለት የማይበገር ተራራ፣ በማንኛውም ማዕበል ውስጥ የማይናወጥ መሪ ነበር። አሜሪካ ለህክምና በተመላለሰ ቁጥር "ይመለሳል" የሚለው ተስፋቸው ፀንቶ ነበር። ቪክቶር ሁጎ "ሞት ማለት መጥፋት ሳይሆን ወደ ሌላ ክፍል መሸጋገር ነው" እንደሚለው ሁሉ፣ አማንም ወደ ሌላው ዓለም ሲሸጋገር በቢሮዎቹ ውስጥ የቀረው ባዶነት ግን የሚሞላ አልነበረም። ሰራተኞቹ ሰኞን የጠበቁት በአካል ሊቀበሉት እንጂ በሀዘን መግለጫ ሊሸኙት አልነበረም።
የአማን ታሪክ ሲነሳ የግዴታ ሌላውን የዓለም ክፍል ማስታወስ ይገባል። በ19ኛው ክፍለ ዘመን አሜሪካዊው የሚዲያ ንጉስ ጆሴፍ ፑሊትዘር ጋዜጠኝነትን ለህዝብ ቅርብ ለማድረግ የታገለው ትግል ከአማን ጋር ይመሳሰላል።
አማንም በ2008 በሜሪላንድ ሲልቨር ስፕሪንግ EBSን ሲመሰርት፣ ዓላማው ዳያስፖራውን ከሀገር ቤት ጋር ማገናኘት ብቻ አልነበረም፤ የኢትዮጵያን ሚዲያ ዘመናዊ ማድረግም እንጂ። ልክ እንደ ፑሊትዘር ሁሉ አማንም በስራው ላይ የሚሰነዘሩ ትችቶችን (መዝናኛ ብቻ ነው፣ ከውጭ የተቀዳ ነው የሚሉትን) በዝምታና በስራ ነበር የሚመልሰው። እሱ የሚያየው ከትችቱ ባሻገር ያለውን ትልቅ ምስል ነበር።
አማን ፍስሃጽዮን ሚዲያን እንደ ተራ መዝናኛ ሳይሆን እንደ "ኢንዱስትሪ" የተመለከተ ቀዳሚ ሰው ነው። በኢትዮጵያ አንድ ለእናቱ በነበረው ኢቲቪ (ETV) ዘመን፣ አማን የሳተላይት ቴሌቪዥን ባህልን ቀይሯል። ሰይፉ በኢቢኤስ፣ አስፋው፣ ነፃነት እና የጠፉ ቤተሰቦችን ፍለጋ ያሉ ፕሮግራሞች በኢትዮጵያውያን ሳሎን ውስጥ አዲስ ንፋስ ነፈሱ። እሱ በHD ጥራት ማሰራጨት ሲጀምር፣ ብዙዎች "ይህ ለኢትዮጵያ ገና ነው" ይሉ ነበር። እሱ ግን "ኢትዮጵያ ለጥራት ዝግጁ ነች" ብሎ ያምን ነበር። ጆርጅ በርናርድ ሾው "አንዳንዶች ነገሮችን ባሉበት ያዩና 'ለምን?' ይላሉ፤ እኔ ግን የሌሉ ነገሮችን አልምና 'ለምን አይሆንም?' እላለሁ" እንዳለው፣ አማንም "ለምን አይሆንም" ባይ ነበር።
በህይወቱ የመጨረሻ ቀናት አማን ስለ ሀገሩ ያለው ጭንቀት ከህመሙ በላይ ነበር። የኢትዮጵያ ቢዝነስ ሪቪው (EBR) እንደገለጸው፣ አማን የኢትዮጵያ ብሮድካስተሮች ማህበር ሰብሳቢ ሆኖ ሲያገለግል ለግል ሚዲያዎች ነፃነትና ዕድገት ተሟግቷል። የውጭ ምንዛሬ እጥረት፣ የሳተላይት ክፍያና የህግ ማዕቀፎች እንቅፋት ቢሆኑበትም፣ እሱ ግን ሁልጊዜም መፍትሄ አፈላላጊ ነበር። "ትዕግስት እና ጥራት" ለወጣቶች የሚሰጠው ትልቁ ምክሩ ነበር። ዛሬ ያ ምክሩ በኢቢኤስ ስቱዲዮዎች ውስጥ እንደ ማሚቶ ያስተጋባል።
አማን ላይ የሚሰነዘሩ ትችቶችም አልጠፉም ነበር። ፕሮግራሞቹ "ዐደንዛዥ" ናቸው፣ ወጣቱን አያነቁም የሚሉ ወገኖች ነበሩ። ነገር ግን አንድ የጥበብ ሰው "ትችት የማይሰነዘርበት ስራ፣ ስራ አይደለም" ይላል። አማን የሰዎችን ቤት በሳቅና በደስታ መሙላቱ፣ የጠፉ ቤተሰቦችን ማገናኘቱና ለብዙ ሺህ ወጣቶች የሥራ ዕድል መፍጠሩ የሚካድ ሀቅ አይደለም። የእሱ ህልም ኢትዮጵያውያን የራሳቸውን ታሪክ በራሳቸው አንደበት እንዲነግሩ ማስቻል ነበር። ይህ ራዕይ ደግሞ ከትችቶች ሁሉ በላይ ግዙፍ ነው።
የካቲት 4 ቀን 2018 ዓ.ም. የኢቢኤስ ማኔጅመንት የአማንን ህልፈት ሲያበስር መላው የሚዲያ ቤተሰብ ደንግጧል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ በሰጡት መግለጫ "አማን ለኢትዮጵያ የግል ሚዲያ ዕድገት ወሳኝ ሚና ከነበራቸው አንዱ ነው" ብለዋል። ይህ ምስክርነት አማን በህይወት ዘመኑ የዘራው ፍሬ ምን ያህል ጥልቅ እንደነበረ ያሳያል። እርግጥ ነው፣ አካሉ በአሜሪካ ቢረግፍም፣ አሻራው ግን በአዲስ አበባ ጎዳናዎችና በኢትዮጵያውያን ልብ ውስጥ ለዘላለም ይኖራል።
በአሁኑ ሰዓት በአሜሪካ ሜሪላንድ ግዛት የሽኝት መርሃ ግብሮች እየተከናወኑ ይገኛሉ። ዛሬ ሐሙስ እና ነገ ዓርብ በታኮማ ፓርክ ወዳጅ ዘመዶቹ ይሰበሰባሉ። ቅዳሜ ደግሞ በጸሎት ይሸኛል። ሁሉም ሰው የሚያወራው ስለ አማን ደግነት፣ ስለ ራዕዩና ስለ ብርቱነቱ ነው። አንቶን ቼኮቭ "ሰው ህያው የሚሆነው በሌሎች ትውስታ ውስጥ እስከኖረ ድረስ ነው" ይላል። አማን በፈጠረው የቴሌቪዥን ጣቢያና በለወጠው የሚዲያ ታሪክ ውስጥ ለዘላለም ህያው ሆኖ ይኖራል።
የቀብር አስፈፃሚ ኮሚቴው አስከሬኑ ወደ ኢትዮጵያ የሚመጣበትን ቀን እያመቻቸ ነው። አማን የተመኘው በሀገሩ አፈር ውስጥ ለማረፍ ነበር። ያ ምኞቱ ሊፈጸም ጥቂት ቀናት ቀርተውታል። የኢቢኤስ ስቱዲዮዎች ዛሬ ባዶ ቢመስሉም፣ የአማን መንፈስ ግን እዚያው አለ። "ራዕዩ ይቀጥላል" ያለው የጣቢያው መግለጫ፣ የአማን ሞት ፍፃሜ ሳይሆን የአዲስ ምዕራፍ ጅምር መሆኑን ያመለክታል።
በመጨረሻም፣ አማን ፍስሃጽዮን 54 ዓመታትን ብቻ አይደለም የኖረው፤ በሚሊዮኖች ልብ ውስጥ የሚቀመጡ በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዓታትን የሚዲያ ታሪክ ነው የሰራው። ከካንሰር ጋር ያደረገው ትግል በአካል ቢሸነፍም፣ በስራውና በታሪኩ ግን አሸናፊ ሆኖ አልፏል። "ኢትዮጵያ መሞት እፈልጋለሁ" ያለው ቃሉ፣ ለሀገሩ ያለውን የከበረ ፍቅር የመጨረሻ መግለጫ ሆኖ ይኖራል። ነፍስ ይማር አማን፤ ስራህ ግን ለዘላለም አይሞትም።