2 hours ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የዛሬ 15 ዓመት ገደማ በፈረንጆቹ ግንቦት 2011፣ በአሜሪካ ዋሽንግተን ግዛት የምትገኝ አንዲት ትንሽ ከተማ በአሰቃቂ ድርጊት ተናወጠች። ከትውልድ አገሯ ኢትዮጵያ የተሻለ ሕይወትና ፍቅር ፍለጋ የመጣችው የ13 ዓመቷ ታዳጊ ሃና አለሙ (Hana Williams)፣ ማንም ሰብዓዊ ፍጡር ሊሸከመው የማይችለውን ስቃይና ፍጹም ጭካኔ በአሳዳጊ ወላጆቿ እጅ ካስተናገደች በኋላ፣ በአንድ ቀዝቃዛ ምሽት በጭቃ ላይ ወድቃ ሕይወቷ አለፈ።
ሃና ከዚህ ዓለም ብትለይም፣ የእሷን አሳዛኝ ታሪክ የሚሰማ ማንኛውም ሰው ልብ ዛሬም ድረስ በሐዘንና በቁጭት ይደማል። ዛሬም ድረስ ብዙዎችን ምሽት ላይ እንቅልፍ የሚነሳው ይህ ታሪክ፣ በቅርቡ በአዲስ አሁናዊ ዜና ወደ አደባባይ መጥቷል።
በዚህ ጉዳይ ላይ የወጣው የመጨረሻውና አሁናዊው መረጃ እንደሚያሳየው፣ ያቺን ንጽሕት ሕፃን በረሃብና በብርድ አሰቃይተው የገደሏት ጨካኞቹ አሳዳጊ ወላጆቿ — ካሪ እና ላሪ ዊሊያምስ—ከተፈረደባቸው የረጅም ዓመታት እስራት ለማምለጥ የሙጥኝ ያሉበት የመጨረሻው የይግባኝ ተስፋቸው ሙሉ በሙሉ ተዘግቷል።
ፍርድ ቤቱ በቅርቡ በሰጠው ውሳኔ፣ ወንጀለኞቹ "በፍርድ ሂደቱ ላይ ስህተት ተፈጽሟል፣ በድጋሚ ይታይልን" በማለት ያቀረቡትን አቤቱታ ውድቅ አድርጎታል። የዋሽንግተን ግዛት ይግባኝ ሰሚ ፍርድ ቤት ባወጣው ባለ ብዙ ገጽ ዝርዝር ውሳኔ፣ የተሰጣቸው የ37 እና የ28 ዓመታት የእስራት ፍርድ ፍጹም ፍትሐዊ መሆኑንና በአንዲት አቅመ-ቢስ ሕፃን ላይ የፈጸሙት ግፍ ይቅር የማይባል መሆኑን በድጋሚ አረጋግጧል። ይህም ማለት ሁለቱም ጨካኝ ወላጆች ዕድሜያቸውን በሙሉ በጠበቀ ጥበቃ ሥር ባሉ የሴቶችና የወንዶች ማረሚያ ቤቶች ውስጥ አሳልፈው ይጨርሳሉ።
ምንም እንኳ የፍርድ ቤቱ ውሳኔ ወንጀለኞቹ ከእስር ቤት አምልጠው በነፃነት አየር እንዳይተነፍሱ ቢያደርግም፣ በጉዲፈቻ ስም ተሰርቆ የጠፋውን የሃናን የልጅነት ጊዜና የተቀጠፈውን ውድ ሕይወቷን መመለስ አይችልም። ዛሬም ድረስ በአሜሪካና በኢትዮጵያ ሕዝብ ልብ ውስጥ ትልቅ ጠባሳ ጥሎ ያለፈው የሃና ታሪክ፣ የሕፃናትን መብት ለማስከበርና መሰል ግፎችን ለመከላከል የሚደረገውን ትግል በሐዘን ማስታወሻነት እየመራ ይገኛል።
ኢሰብዓዊ በሆነ መንገድ ምድራዊ ፍቅር የተነፈገችው ሃና አለሙ፣ ዛሬ ካለችበት ዓለም ሆና ወንጀለኞቿ ከእስር ቤት የብረት ዘንጎች በስተጀርባ ሆነው ዋጋቸውን ሲከፍሉ እያየች ይሆን? ብዙዎች አሁንም የሚመኙት አንድ ነገር ብቻ ነው — ይህች ንጽሕት ነፍስ በምድር ላይ ያጣችውን ሰላምና እቅፍ በሰማይ አግኝታ ለዘላለም እንድታርፍ። ክሪሚናል ማተር የተሰኘው የሰብ አዊ መብት ተሟጋች ዛሬ ባወጣው ጽሑፍ "የ13 ዓመቷ የሃና ግሬስ-ሮዝ ዊሊያምስ ታሪክ እውነቱን ለመናገር ሌሊት እንቅልፍ የሚነሳኝ እና ዕረፍት የሚያሳጣኝ ታሪክ ነው። የተሻለ ሕይወት ታገኛለች በሚል ተስፋ ከኢትዮጵያ በጉዲፈቻ ወደ አሜሪካዋ ዋሽንግተን ግዛት ብትወሰድም፣ የገጠማት ግን ሊታሰብ የማይችል ዘግናኝ ጭካኔ ነበር። አሳዳጊ ወላጆቿ የሆኑት ካሪ እና ላሪ ዊሊያምስ ባደረሱባት በደል እና እንግልት፣ እ.ኤ.አ. በ2011 በከፍተኛ ቅዝቃዜ (Hypothermia) ምክንያት ለሞት እንድትዳረግ በማድረጋቸው ጥፋተኛ ተብለው ተፈርዶባቸዋል።
ሊጠብቋት እና ሊንከባከቧት ኃላፊነት በወሰዱ ሰዎች፣ እንዲህ ባለች ምስኪን ልጅ ላይ እንዴት ይህን ያህል ኢ-ሰብዓዊ ድርጊት ሊፈጸም እንደቻለ ለማሰብ እና ለመቀበል ይከብደኛል። በዚህች ምድር ላይ የተነፈገችውን ሰላም በመጨረሻው ዓለም እንዳገኘችው ተስፋ አደርጋለሁ።" ብሏል።
ሃና ከዚህ ዓለም ብትለይም፣ የእሷን አሳዛኝ ታሪክ የሚሰማ ማንኛውም ሰው ልብ ዛሬም ድረስ በሐዘንና በቁጭት ይደማል። ዛሬም ድረስ ብዙዎችን ምሽት ላይ እንቅልፍ የሚነሳው ይህ ታሪክ፣ በቅርቡ በአዲስ አሁናዊ ዜና ወደ አደባባይ መጥቷል።
በዚህ ጉዳይ ላይ የወጣው የመጨረሻውና አሁናዊው መረጃ እንደሚያሳየው፣ ያቺን ንጽሕት ሕፃን በረሃብና በብርድ አሰቃይተው የገደሏት ጨካኞቹ አሳዳጊ ወላጆቿ — ካሪ እና ላሪ ዊሊያምስ—ከተፈረደባቸው የረጅም ዓመታት እስራት ለማምለጥ የሙጥኝ ያሉበት የመጨረሻው የይግባኝ ተስፋቸው ሙሉ በሙሉ ተዘግቷል።
ፍርድ ቤቱ በቅርቡ በሰጠው ውሳኔ፣ ወንጀለኞቹ "በፍርድ ሂደቱ ላይ ስህተት ተፈጽሟል፣ በድጋሚ ይታይልን" በማለት ያቀረቡትን አቤቱታ ውድቅ አድርጎታል። የዋሽንግተን ግዛት ይግባኝ ሰሚ ፍርድ ቤት ባወጣው ባለ ብዙ ገጽ ዝርዝር ውሳኔ፣ የተሰጣቸው የ37 እና የ28 ዓመታት የእስራት ፍርድ ፍጹም ፍትሐዊ መሆኑንና በአንዲት አቅመ-ቢስ ሕፃን ላይ የፈጸሙት ግፍ ይቅር የማይባል መሆኑን በድጋሚ አረጋግጧል። ይህም ማለት ሁለቱም ጨካኝ ወላጆች ዕድሜያቸውን በሙሉ በጠበቀ ጥበቃ ሥር ባሉ የሴቶችና የወንዶች ማረሚያ ቤቶች ውስጥ አሳልፈው ይጨርሳሉ።
ምንም እንኳ የፍርድ ቤቱ ውሳኔ ወንጀለኞቹ ከእስር ቤት አምልጠው በነፃነት አየር እንዳይተነፍሱ ቢያደርግም፣ በጉዲፈቻ ስም ተሰርቆ የጠፋውን የሃናን የልጅነት ጊዜና የተቀጠፈውን ውድ ሕይወቷን መመለስ አይችልም። ዛሬም ድረስ በአሜሪካና በኢትዮጵያ ሕዝብ ልብ ውስጥ ትልቅ ጠባሳ ጥሎ ያለፈው የሃና ታሪክ፣ የሕፃናትን መብት ለማስከበርና መሰል ግፎችን ለመከላከል የሚደረገውን ትግል በሐዘን ማስታወሻነት እየመራ ይገኛል።
ኢሰብዓዊ በሆነ መንገድ ምድራዊ ፍቅር የተነፈገችው ሃና አለሙ፣ ዛሬ ካለችበት ዓለም ሆና ወንጀለኞቿ ከእስር ቤት የብረት ዘንጎች በስተጀርባ ሆነው ዋጋቸውን ሲከፍሉ እያየች ይሆን? ብዙዎች አሁንም የሚመኙት አንድ ነገር ብቻ ነው — ይህች ንጽሕት ነፍስ በምድር ላይ ያጣችውን ሰላምና እቅፍ በሰማይ አግኝታ ለዘላለም እንድታርፍ። ክሪሚናል ማተር የተሰኘው የሰብ አዊ መብት ተሟጋች ዛሬ ባወጣው ጽሑፍ "የ13 ዓመቷ የሃና ግሬስ-ሮዝ ዊሊያምስ ታሪክ እውነቱን ለመናገር ሌሊት እንቅልፍ የሚነሳኝ እና ዕረፍት የሚያሳጣኝ ታሪክ ነው። የተሻለ ሕይወት ታገኛለች በሚል ተስፋ ከኢትዮጵያ በጉዲፈቻ ወደ አሜሪካዋ ዋሽንግተን ግዛት ብትወሰድም፣ የገጠማት ግን ሊታሰብ የማይችል ዘግናኝ ጭካኔ ነበር። አሳዳጊ ወላጆቿ የሆኑት ካሪ እና ላሪ ዊሊያምስ ባደረሱባት በደል እና እንግልት፣ እ.ኤ.አ. በ2011 በከፍተኛ ቅዝቃዜ (Hypothermia) ምክንያት ለሞት እንድትዳረግ በማድረጋቸው ጥፋተኛ ተብለው ተፈርዶባቸዋል።
ሊጠብቋት እና ሊንከባከቧት ኃላፊነት በወሰዱ ሰዎች፣ እንዲህ ባለች ምስኪን ልጅ ላይ እንዴት ይህን ያህል ኢ-ሰብዓዊ ድርጊት ሊፈጸም እንደቻለ ለማሰብ እና ለመቀበል ይከብደኛል። በዚህች ምድር ላይ የተነፈገችውን ሰላም በመጨረሻው ዓለም እንዳገኘችው ተስፋ አደርጋለሁ።" ብሏል።
1 day ago
በሀገር ውስጥ አቅም ውስብስብ የልብ ቀዶ ጥገናን በተሳካ ሁኔታ ማካሄድ መቻሉ ተገለፀ
****************
በኢትዮጵያ የልብ ሕሙማን ሕፃናት መርጃ ለሁለት ሕፃናት ህይወታቸውን የሚታደግ ውስብስብ የልብ ቀዶ ጥገና በተሳካ ሁኔታ ማካሄዱን ገለፀ።
ቀዶ ጥገናው የተደረገው ለ6 ዓመት እና ለ8 ወር ሕፃናት ሲሆን፣ ከቀዶ ጥገና ህክምናው በኋላ የህጻናቱ ጤንነት በመልካም ሁኔታ ላይ እንደሚገኝ ተገልጿል።
ህክምናውን በዶክተር ፍፁም አርጋው የሚመራ የሀገር ውስጥ የልብ ቀዶ ጥገና ቡድን የመራው ሲሆን፣ በዶክተር ሜሮን ተስፋዬ የሚመራው የፅኑ ህክምና ቡድንም ለህፃናቱ ማገገሚያ የሚሆን ልዩ ክትትል እያደረገ መሆኑን ከማዕከሉ ያገኘነው መረጃ አመልክቷል።
እንዲህ ያሉ ውስብስብ የልብ ቀዶ ጥገናዎች በሀገር ውስጥ መከናወናቸው የህፃናትን ሕይወት ከመታደግ ባለፈ የሀገሪቱን የልብ ሕክምና አቅም እየጎለበተ ስለመሆኑ የሚያሳይ ነው ተብሏል።
በኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት ከ7,000 በላይ ታካሚ ሕፃናት የልብ ቀዶ ጥገና ለማግኘት በረጅም የተጠባባቂነት ሰልፍ ላይ ይገኛሉ።
እንደዚህ ያሉ ውስብስብ ቀዶ ጥገናዎች በውጭ ሀገራት ለማካሄድ እስከ ሺዎች ዶላር የሚጠይቁ በመሆናቸው፣ ማዕከሉ በነጻ የሚሰጠው ይህ አገልግሎት ለታካሚ ቤተሰቦች ከፍተኛ የፋይናንስ እፎይታን ሰጥቷል።
ከዚህም በላይ የውጭ ሀገር የበጎ አድራጎት ቡድኖችን ሳይጠብቁ በሀገር ውስጥ የልብ ስፔሻሊስቶች አቅም ብቻ መከናወኑ ኢትዮጵያ በዘርፉ ያላትን የሕክምናና የቴክኖሎጂ አቅም ወደ አዲስ ደረጃ ማሸጋገሯን ማሳያ መሆኑ ተጠቅሷል።
በኢንቲሀድ አብራር
****************
በኢትዮጵያ የልብ ሕሙማን ሕፃናት መርጃ ለሁለት ሕፃናት ህይወታቸውን የሚታደግ ውስብስብ የልብ ቀዶ ጥገና በተሳካ ሁኔታ ማካሄዱን ገለፀ።
ቀዶ ጥገናው የተደረገው ለ6 ዓመት እና ለ8 ወር ሕፃናት ሲሆን፣ ከቀዶ ጥገና ህክምናው በኋላ የህጻናቱ ጤንነት በመልካም ሁኔታ ላይ እንደሚገኝ ተገልጿል።
ህክምናውን በዶክተር ፍፁም አርጋው የሚመራ የሀገር ውስጥ የልብ ቀዶ ጥገና ቡድን የመራው ሲሆን፣ በዶክተር ሜሮን ተስፋዬ የሚመራው የፅኑ ህክምና ቡድንም ለህፃናቱ ማገገሚያ የሚሆን ልዩ ክትትል እያደረገ መሆኑን ከማዕከሉ ያገኘነው መረጃ አመልክቷል።
እንዲህ ያሉ ውስብስብ የልብ ቀዶ ጥገናዎች በሀገር ውስጥ መከናወናቸው የህፃናትን ሕይወት ከመታደግ ባለፈ የሀገሪቱን የልብ ሕክምና አቅም እየጎለበተ ስለመሆኑ የሚያሳይ ነው ተብሏል።
በኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት ከ7,000 በላይ ታካሚ ሕፃናት የልብ ቀዶ ጥገና ለማግኘት በረጅም የተጠባባቂነት ሰልፍ ላይ ይገኛሉ።
እንደዚህ ያሉ ውስብስብ ቀዶ ጥገናዎች በውጭ ሀገራት ለማካሄድ እስከ ሺዎች ዶላር የሚጠይቁ በመሆናቸው፣ ማዕከሉ በነጻ የሚሰጠው ይህ አገልግሎት ለታካሚ ቤተሰቦች ከፍተኛ የፋይናንስ እፎይታን ሰጥቷል።
ከዚህም በላይ የውጭ ሀገር የበጎ አድራጎት ቡድኖችን ሳይጠብቁ በሀገር ውስጥ የልብ ስፔሻሊስቶች አቅም ብቻ መከናወኑ ኢትዮጵያ በዘርፉ ያላትን የሕክምናና የቴክኖሎጂ አቅም ወደ አዲስ ደረጃ ማሸጋገሯን ማሳያ መሆኑ ተጠቅሷል።
በኢንቲሀድ አብራር
2 days ago
ኢትዮ-ኢስታንቡል ሆስፒታል በዓመት ከ79 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች ህክምና መስጠቱን ገለጸ
#ethiopia | ኢትዮ-ኢስታንቡል ጠቅላላ ሆስፒታል በተመሰረተ በአጭር ጊዜ ወደውጭ ሀገር በሚወስዱ የህክምና ጥገኝነትን በመቀየር፣ በሀገር ውስጥ ዘመናዊ ህክምና መስጠት የሚያስችል አገልግሎት መዘርጋቱን አስታወቀ።
ኢትዮ-ኢስታንቡል አጠቃላይ ሆስፒታል ሐምሌ 28 ቀን 2018 ዓ.ም ለመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች በሰጠው መግለጫ ላይ እንደተገለጸው ሆስፒታሉ በመሥራቹና ባለራዕዩ ሲኢኦ አቶ ብርሃን ተድላ እየተመራ ከተመሰረተበት ጊዜ ጀምሮ ለታካሚዎች ጥራቱን የጠበቀ የሕክምና አገልግሎት ሲሰጥ የቆየ ሲሆን፣ በተለይም በያዝነው 2018 ዓ.ም ብቻ ከ79 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የተመላላሽ ህክምና አገልግሎት በመስጠትና ከ4 ሺ 500 በላይ የቀዶ ህክምናዎችን በማካሄድ አመርቂ ውጤት አስመዝግቧል።
ሆስፒታሉ እነዚህን ሀገር በቀል አቅሞች በመገንባቱ ቀደም ሲል ለህክምና ወደ ውጭ ሀገር ይሄዱ የነበሩ ታካሚዎችን ቁጥር በመቀነስ የውጭ ምንዛሬን ከማስቀረት ባሻገር የታካሚዎችን ችግር መቅረፍ ችሏል።
በመግለጫው ወቅት የሆስፒታሉ ሜዲካል ዳይሬክተር፣ የአጠቃላይ እና ደረት አካባቢ ቀዶ ህክምና ስፔሻሊስት ተባባሪ ኘሮፌሰር ስዩም ካሣ መርኔ እንደገለጹት፣ ተቋሙ በኢንተርቬንሽናል ካርዲዮሎጂ መስክ ያለ ኦፕሬሽን በደም ስሮች በኩል በሚደረግ ህክምና ጨምሮ በአዋቂና በልጆች የልብ ሕክምና በአጠቃላይ ከ735 በላይ ታካሚዎችን መታደግ ችሏል። አክለውም ይህ አገልግሎት ዓመቱን ሙሉ ሌሊትና ቀን ሳይቋረጥ የሚሰጥ በመሆኑ፣ ከውጭ ሀገር በሚመጡ ጊዜያዊ ዘመቻዎች ላይ ብቻ ጥገኛ የነበረውን አሰራር መቀየር መቻሉን ገልጸዋል።
ሆስፒታሉ በኢትዮጵያውያን ባለሙያዎች በመታገዝ ወደውጪ ሀገር የሚያስኬዱ በተለይ የልብ ሕክምናዎችን 90 በመቶ በሆስፒታሉ መስጠት መቻሉን ጠቅሰዋል።
እንደ ዶክተር ስዩም ገለጻ፣ ሆስፒታሉ በኒውሮሰርጀሪ፣ በኦፕን ካርዲያክ፣ በአጥንትና ስፓይን፣ በኩላሊት፣ በሳምባ፣ የአንጎል፣ የዳሌና የጉልበት ቅየራ እንዲሁም በሚኒማሊ ኢንቬሲቭ (ላፓሮስኮፒክና ቶራኮስኮፒክ) እና ከ46 በላይ ሰብስፔሻሊቲ ህክምና ዘርፎች የላቀ አገልግሎት እየሰጠ ሲሆን፣ የሬዲዮሎጂ ክፍሉም የሰው ሰራሽ አስተውሎት ቴክኖሎጂን በመጠቀም የህክምና ምርመራ ጥራቱን በማሳደግ ላይ ይገኛል ብለዋል።
የሆስፒታሉ የውስጥ ደዌና የአዋቂዎች ኢንተርቬንሽናል የልብ ህክምና ስፔሻሊስት ዶክተር ከፈለኝ ደጀኔ በበኩላቸው እንደገለጹት፣ ከተሰሩት 321 የሕፃናት የልብ ህክምናዎች መከናወናቸውን ጠቁመው 90 የሚጠጋ ድንገተኛ የልብ ደምስር መዘጋት አደጋ ያጋጠማቸውና ታካሚዎች በ24 ሰዓት ድንገተኛ አደጋዎች አገልግሎት ህይወታቸው መታደግ ተችላል ብለዋል። ከእነዚህም ውስጥ ቁጥራቸው ከ90 በላይ የሚኾኑ የውጭ ሀገር ዜጎችና ዲፕሎማቶች እንዲሁም ነፍሰጡር እናቶች ይገኙበታል።
የሆስፒታሉ የቺፍ ኦፕሬሽንስ ዳይሬክተር፣ የአንገትና ጭንቅላት ሰብ-ስፔሻሊስት ዶክተር መለስ ገበየሁ እንደገለጹት ደግሞ፣ ተቋሙ ከንግድ ዓላማው ጎን ለጎን ማህበራዊ ኃላፊነቱን በመወጣት ረገድ ትልቅ ስራ እየሰራ ይገኛል። በሆስፒታሉ ባለቤትና ዋና ስራአስፈጻሚ አቶ ብርሃን ተድላ አማካይነት በተቋቋመው "Heart to Heart Children's Aid" የተሰኘ ፋውንዴሽን በኩል ትልቅ ሥራዎች መከናወናቸውን አስታውሰዋል።
ሜዲካል ዳይሬክተሩ በመጨረሻም ኢትዮ ኢስታንቡል ጠቅላላ ሆስፒታል በሰኔ ወር 2015 ዓ.ም ጀምሮ ወደሥራ መግባቱና በአጭር ጊዜ ውስጥ ከፍተኛ ውጤት መድረስ የቻለው በተቋሙ መስራችና ሲኢኦ አቶ ብርሃን ተድላ የቅርብ ጠንካራ አመራርና ክትትል፣ በሰራተኞችና ባለሙያዎች ትጋት መኾኑን በመጥቀስ ምስጋና አቅርበዋል።
ሆስፒታሉ ለ 333 ጊዜያዊና ቋሚ ሰራተኞች የሥራ ዕድል የፈጠረ ሲኾን ከእነዚህ መካከል 86 ያህሉ ሰብስፔሻስት ሐኪሞች መኾናቸው ተነግሯል።
#ethioistanbulhospital #cardiologyservices
#pediatriccardiolog #healthsectorethiopia
#medicaltourismethiopia#hearttoheartchildrensaid
#ethiopia | ኢትዮ-ኢስታንቡል ጠቅላላ ሆስፒታል በተመሰረተ በአጭር ጊዜ ወደውጭ ሀገር በሚወስዱ የህክምና ጥገኝነትን በመቀየር፣ በሀገር ውስጥ ዘመናዊ ህክምና መስጠት የሚያስችል አገልግሎት መዘርጋቱን አስታወቀ።
ኢትዮ-ኢስታንቡል አጠቃላይ ሆስፒታል ሐምሌ 28 ቀን 2018 ዓ.ም ለመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች በሰጠው መግለጫ ላይ እንደተገለጸው ሆስፒታሉ በመሥራቹና ባለራዕዩ ሲኢኦ አቶ ብርሃን ተድላ እየተመራ ከተመሰረተበት ጊዜ ጀምሮ ለታካሚዎች ጥራቱን የጠበቀ የሕክምና አገልግሎት ሲሰጥ የቆየ ሲሆን፣ በተለይም በያዝነው 2018 ዓ.ም ብቻ ከ79 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የተመላላሽ ህክምና አገልግሎት በመስጠትና ከ4 ሺ 500 በላይ የቀዶ ህክምናዎችን በማካሄድ አመርቂ ውጤት አስመዝግቧል።
ሆስፒታሉ እነዚህን ሀገር በቀል አቅሞች በመገንባቱ ቀደም ሲል ለህክምና ወደ ውጭ ሀገር ይሄዱ የነበሩ ታካሚዎችን ቁጥር በመቀነስ የውጭ ምንዛሬን ከማስቀረት ባሻገር የታካሚዎችን ችግር መቅረፍ ችሏል።
በመግለጫው ወቅት የሆስፒታሉ ሜዲካል ዳይሬክተር፣ የአጠቃላይ እና ደረት አካባቢ ቀዶ ህክምና ስፔሻሊስት ተባባሪ ኘሮፌሰር ስዩም ካሣ መርኔ እንደገለጹት፣ ተቋሙ በኢንተርቬንሽናል ካርዲዮሎጂ መስክ ያለ ኦፕሬሽን በደም ስሮች በኩል በሚደረግ ህክምና ጨምሮ በአዋቂና በልጆች የልብ ሕክምና በአጠቃላይ ከ735 በላይ ታካሚዎችን መታደግ ችሏል። አክለውም ይህ አገልግሎት ዓመቱን ሙሉ ሌሊትና ቀን ሳይቋረጥ የሚሰጥ በመሆኑ፣ ከውጭ ሀገር በሚመጡ ጊዜያዊ ዘመቻዎች ላይ ብቻ ጥገኛ የነበረውን አሰራር መቀየር መቻሉን ገልጸዋል።
ሆስፒታሉ በኢትዮጵያውያን ባለሙያዎች በመታገዝ ወደውጪ ሀገር የሚያስኬዱ በተለይ የልብ ሕክምናዎችን 90 በመቶ በሆስፒታሉ መስጠት መቻሉን ጠቅሰዋል።
እንደ ዶክተር ስዩም ገለጻ፣ ሆስፒታሉ በኒውሮሰርጀሪ፣ በኦፕን ካርዲያክ፣ በአጥንትና ስፓይን፣ በኩላሊት፣ በሳምባ፣ የአንጎል፣ የዳሌና የጉልበት ቅየራ እንዲሁም በሚኒማሊ ኢንቬሲቭ (ላፓሮስኮፒክና ቶራኮስኮፒክ) እና ከ46 በላይ ሰብስፔሻሊቲ ህክምና ዘርፎች የላቀ አገልግሎት እየሰጠ ሲሆን፣ የሬዲዮሎጂ ክፍሉም የሰው ሰራሽ አስተውሎት ቴክኖሎጂን በመጠቀም የህክምና ምርመራ ጥራቱን በማሳደግ ላይ ይገኛል ብለዋል።
የሆስፒታሉ የውስጥ ደዌና የአዋቂዎች ኢንተርቬንሽናል የልብ ህክምና ስፔሻሊስት ዶክተር ከፈለኝ ደጀኔ በበኩላቸው እንደገለጹት፣ ከተሰሩት 321 የሕፃናት የልብ ህክምናዎች መከናወናቸውን ጠቁመው 90 የሚጠጋ ድንገተኛ የልብ ደምስር መዘጋት አደጋ ያጋጠማቸውና ታካሚዎች በ24 ሰዓት ድንገተኛ አደጋዎች አገልግሎት ህይወታቸው መታደግ ተችላል ብለዋል። ከእነዚህም ውስጥ ቁጥራቸው ከ90 በላይ የሚኾኑ የውጭ ሀገር ዜጎችና ዲፕሎማቶች እንዲሁም ነፍሰጡር እናቶች ይገኙበታል።
የሆስፒታሉ የቺፍ ኦፕሬሽንስ ዳይሬክተር፣ የአንገትና ጭንቅላት ሰብ-ስፔሻሊስት ዶክተር መለስ ገበየሁ እንደገለጹት ደግሞ፣ ተቋሙ ከንግድ ዓላማው ጎን ለጎን ማህበራዊ ኃላፊነቱን በመወጣት ረገድ ትልቅ ስራ እየሰራ ይገኛል። በሆስፒታሉ ባለቤትና ዋና ስራአስፈጻሚ አቶ ብርሃን ተድላ አማካይነት በተቋቋመው "Heart to Heart Children's Aid" የተሰኘ ፋውንዴሽን በኩል ትልቅ ሥራዎች መከናወናቸውን አስታውሰዋል።
ሜዲካል ዳይሬክተሩ በመጨረሻም ኢትዮ ኢስታንቡል ጠቅላላ ሆስፒታል በሰኔ ወር 2015 ዓ.ም ጀምሮ ወደሥራ መግባቱና በአጭር ጊዜ ውስጥ ከፍተኛ ውጤት መድረስ የቻለው በተቋሙ መስራችና ሲኢኦ አቶ ብርሃን ተድላ የቅርብ ጠንካራ አመራርና ክትትል፣ በሰራተኞችና ባለሙያዎች ትጋት መኾኑን በመጥቀስ ምስጋና አቅርበዋል።
ሆስፒታሉ ለ 333 ጊዜያዊና ቋሚ ሰራተኞች የሥራ ዕድል የፈጠረ ሲኾን ከእነዚህ መካከል 86 ያህሉ ሰብስፔሻስት ሐኪሞች መኾናቸው ተነግሯል።
#ethioistanbulhospital #cardiologyservices
#pediatriccardiolog #healthsectorethiopia
#medicaltourismethiopia#hearttoheartchildrensaid
2 days ago
መዝሙረ ሄላም ላይ የተደረገ አጭር ኂሳዊ ንባብ
ከቢኒያም አቡራ
#ethiopia | አዳም ረታ ታሪክን ከነገሥታት፣ ከመሪዎች፣ ማኅበረሰቡ ባበጀው ድልድል ውስጥ ‹ላዕላይ› ከሚባሉት ደረጃዎች አንጻር አያስመለክተንም። ታሪካዊ ከሚባሉ አጋጣሚዎች ውስጥ የተዘነጉትን ጥቃቅን የታሪክ ኹነተ-ደቂቅ (micro-events) ይመርጣል። ይወስዳል መንገድ ላይ … “ቀዳዳ” በተሰኘው ታሪክ ላይ ፍንዳታውን ከሚሞት ዘመድ፣ ከሚደነግጥ ለማኝ፣ ከሚሰነጠቅ የወፍ እንቁላል፣ ከሚፈስ የእናት ወተት ጋር Micro-Macro Connection በመፍጠር የትልቁ ቀዳዳ መፈጠርን ከሚጢጢዬ ሽንቁሮች ጋር ያስተሳስርልናል። እንዲህ ያሉ የኒው ሂስቶሪሲዝም ባሕሪያትን ከዚህ ቀደም ባሳተማቸው መጻሕፍቱ ውስጥ በተለያየ መጠን እናገኛለን።
Adam Reta አዳም ረታ "መዝሙረ ሄላም" በተሰኘው በዐዲሱ መጽሐፉ ላይም በኢትዮጵያ ታሪካዊ-ፖለቲካዊ አጋጣሚ ውስጥ እንደ ዐውራ የሚታዩትን የእድገት በኅብረት ዘመቻን እንደነ-አሮን፣ እንደነቃል … ባሉ ገጸባሕርያት በኩል፣ የሰባ ሰባቱን ድርቅ በሄላም ጡት በኩል፣ “ጥላሁን ለምን ለምን ሞተ” እየተባለ ኢዮቤልዩ ቤተመንግሥት ጋር የተደረገውን ሰላማዊ ሰልፍ በሡልጣን በኩል፣ የከተማ መሬት ዐዋጅን በተለያዩ ግለሰቦች በኩል … እናያለን። በዚህም የታሪክን ትልቅ ካርታ ለመረዳት የተረሱና የጠለሉ ታሪኮችን ይመረምራል። ስለዚህ ነቁጣዊ ማኅበራዊ ክስተቶችን ወደ ታሪክ ምኩራብ በማምጣት ከትልቁ የታሪክ ምሥል ጎን ያስተያያል። ይህ ደግሞ የኒው ሂስቶሪሲዝም ኹነኛ ማጠንጠኛ ነው።
ልክ “ይወስዳል መንገድ ያመጣል መንገድ …” በተሰኘው መጽሐፉ ውስጥ ባለው “የመንግሥቱ ጊዜ” በሚለው ድርሰት ውስጥ፣ ትልቁን “የታኅሣሥ ግርግር”ን እንደ መቼት አምጥቶ የተጻፈውና የተተኮረው ግን ኹነተ-ደቂቅ (micro-events) ላይ ነው። ስለግርማሜ ንዋይ፣ ስለኮሌኔል ወርቅነህ ገበየሁ፣ ሰለጄነራል ሙልጌታ ቡሊ አይደለም የሚያትተው። ስለአንድ ብላቴና ከእንቅልፍ መነሳት፣ ስለገበጣ ጨዋታ፣ ቤተክርስቲያን ውስጥ ሕፃናትን አሰብስቦ ‹ኪራላይሶን› የሚያስብል ካሕን፣ ስለመንደር ውስጥ ሐሜቶች፣ ስለግለሰቦች ፍርሃት፣ በአጋጣሚ ስላየው አስደናቂ አሞራ … ያወጋል። የታሪክ አጋጣሚ አምጥቶ በታሪክ ውስጥ ግለሰቦች ላይ ስለሚረብበው የታሪክ መንፈስ ያትታል። ልክ እንደዚሁ መዝሙረ ሄላም ላይም ጽሑፉ ታሪክን አያብራራም፤ ነገር ግን ታሪክ እንዴት በሰው ልብ ውስጥ እንደሚኖር ያሳያል። በዚህ ኹነተ-ደቂቅ (micro-event) ምክንያት በዘመኑ ላይ ያገነገነውን ባሕላዊ እምነትን፣ የሥልጣን መዋቅርን፣ የወል ግንዛቤን አጨንቁረን እንድንመለከት ያስችለናል።
ከመንግሥት ሼልፍ ላይ ሳይኾን ከግለሰብ ጀርባ ላይ የተወሰደው የአዳም የአጻጻፍ መንገድ ከኒው ሂስቶሪስዝም ጽንሰ-ሐሳቦች ጋር በአንድ መም ላይ የሚሄዱ ናቸው። መዝሙረ ሄላም የተሰኘው ዐዲሱ የአዳም ረታ መጽሐፍ የኒው ሂስቶሪሲዝም ባሕርያትን ይጋራል። አንዳንድ ነገሮችን በዓይን መመልከት ባይቻልም በግብሩ (ቁስ ላይ በሚያደርገው ግፊት) ግን ይታወቃል። በመዝሙረ ሄላም መጽሐፍ ውስጥም አንዳንድ ነገሮችን በቀጥታ ማየት ባንችልም ቅሉ እነርሱን የሚያሳይልንን ነገሮች ግን እንቃኛለን። ዘማች ወጣት ተማሪዎችን እናያለን፤ መንግሥትን፣ ሕግንና ኃይልን ግን በቀጥታ አንመለከትም። የተማከለ ኃይል አናይም ግን የገጸባሕርያቱ የፍርሃት ምንጭ ከተማከለ ኃይል ጋር የተያያዘ ቀጭን መስመር መኖሩን እናያለን። መንግሥትም ቢኾን በቀጥታ አይገባም፤ ነገር ግን ፍርሃት እንደ ሥርዓት ዘዋሪ (system driver) ይኾናል። እንደ ሚሸል ፉኮ አገላለጽ ኃይል ከተማከለ ሥርዓት የሚመነጭ ሳይኾን በየትኛውም ቦታና ጊዜ በፍርሃት፣ በልማድ፣ በንግግር … ሊከሰት የሚችል ሂደት አይደል?
መዝሙረ ሄላም ላይ ታሪክ እንደ “circulation of social energy” ቀርቧል። መዝሙረ ሄላም ላይ መረጃ ከመንግሥት አይመጣም፤ ከግለሰብ እንጂ። የከተማ መሬት ዐዋጅም ኾነ የተማሪዎች ዘመቻ በገጸባሕርያቱ ወሬ ውስጥ ነው የሚንቀረቀበው። ይህ የመረጃ ሥርዓት ኃይል ማን እንዳለው ማን እንደሌለው ያሳያል። እንግዲህ ይህ በፉኮኛ micro-power መኾኑ ነው። በመዝሙረ ሄላም ላይ ታሪክ እንደ ወሬ እንጂ እንደ ሰነድ አይቀርብም።
ወሬ የፍርሃት ቤንዚን ነው … ፍርሃት ደግሞ በዝምታ መሸበብን ይፈጥራል … የዝምታ አፈ-ሙቅ ደግሞ ኃይለኛው እንዳይታይ ያደርጋል … የተደራጀው ኃይል ጥፋትን ሊያደርስ ባሰበ ቁጥር የወሬ ቤንዚን ይጨምራል። ሰዎች በዕቅብተ-ንግግር ራሳቸውን ሲሸብቡ ደርዝ ያለው ሙግት ይኮሰምናል፣ ንግግር ሲጠፋ ያልታወቀ አደጋ ይከሰታል፣ ፍርሃትም ይጨምራል። ያልታወቀ አደጋ ደግሞ ከታወቀ አካል ይመጣል። ስለዚህ ጥንስሱ የሚጀምረው ከወሬ እንደኾነ ያስመለክተናል። አዳም በመዝሙረ ሄላም ላይ ታሪክን እንደ “circulation of social energy” ሲያቀርብ ፕሬዝዳንት፣ ጀነራል፣ ፕሮፌሰር የኾኑ ታሪክ ከላዕላይ ያስቀመጣቸው ሰዎች አያስፈልጉትም። በአንጻሩ ሄላም ለማን እንደሳመችው ተደርጎ ብርሃኔ ያስወራው ወሬ፣ የሄላም አባት ወታደር በመኾኑ ምክንያት በካሱ፣ በሄኖክ እናት የተነዛው ወሬ እና ሄላም ከሄኖክ ጋር የተቆራረጠችበት መንገድ እንዲሁም የሄላምን የጡት ወተት በተመለከተ የተነዛው ወሬን ይጠቀማል።
መዝሙረ ሄላምን ከድኅረ-ቅኝ-አገዛዝ የኂስ መንገድ አንጻር እንመልከተው።
እውን ቅኝ-ግዛት ተረት ኾኖ ቀርቷል? በፖለቲካ፣ በኢኮኖሚ፣ በሥነልቦና ረገድ የቅኝ አገዛዝ ዳናው ሙሉ ለሙሉ ጠፍቷል? አዳም በመዝሙረ ሄላም ጽሑፍ ውስጥ ከቅኝ-ግዛት በተወረሰ መዋቅር ምክንያት የተሰናከለን ሕይወት ሊያስመለክተን ይኾን?
“ከተሞች ከቅኝ ግዛት በኋላ ሁለት ዓይነት መልክ ይኖራቸዋል፤ ለጥቂቱ የተድላ፣ ለተቀረው ደግሞ የአሳር መንደር ይኾናሉ” ይላል ፍራንዝ ፋኖን። በመዝሙረ ሄላም ላይ እና “የቢሾፍቱ ልጆች ጥላሞት” የተሰኘው ድርሰት ላይም ይህንን ነው የምንመለከተው። “ይወስዳል መንገድ ያመጣል መንገድ …” በተሰኘው መጽሐፉ ውስጥ ካሉ ጽሑፎች መካከል “የቢሾፍቱ ልጆች ጥላ ሞት” አንዱ ነው። የቢሾፍቱ ልጆች ሆቴሉን ያዩታል፤ ግን አይገቡበትም። ሆቴሉ የሀገራቸው መሬት ላይ ነው፤ እነርሱ ግን ከሆቴሉ ውጭ ናቸው። መናፈሻው ውስጥ አንዲት የፈረንጅ ልጅ ጠግባ ለልጆቹ እንደ ውሻ ዳቦ ትወረውርላቸዋለች። አፈር ላይ የወደቀን ዳቦ አራግፈው ይመገባሉ። በገዛ ሐይቃቸው ዳር ላይ ናቸው፤ ሌሎች ግን በጀልባ እየተንሸራሸሩ ይንፈላሰሳሉ። ለፈረንጆቹ ያደረው ሞገስ የላንድሮቨር ተፈናጣጭ ኾኗል። ሌሎቹ ግን ከመኪናው ውጪ ናቸው። ሞገስ እንደ እነርሱ ሕጻን ቢኾንም ለፈረንጅ በማሸርገዱ የትምህርት ቤቱ ባለቤት ሲመስል ሌሎች ልጆች ግን በገዛ መምህራቸው ይብጠለጠላሉ። የቢሾፍቱ ልጆች፣ ነጻ በተባለች ሀገር እየኖሩ በቅኝ ግዛት ጥላ ይተዳደራሉ። የቢሾፍቱ ልጆች በገዛ መንደራቸው አካሉ በማይታይ የቅኝ ግዛት እጅ ይገፋሉ። ሞገስ አይናገርም፤ የሚናገርለት አለ። ልክ የቢሾፍቱ ልጆች ላይ በአንድ ከተማ ውስጥ ሁለት የከተማ ምሥል እንደምናገኘው ሁሉ “የስንብት ቀለማት” ላይም በአዲስ አበባ ውስጥ ሁለት የከተማ ምሥል እንመለከታለን። እንደ ዘድሬክ፣ ሳተርን፣ ከተስፋዬ ወደ አሸናፊ የተቀየሩ የድሎት ምሥሎች እና የእነምትክ ጉልት፣ የእትየ እልልታ የጉርሻ መሸጫ መስኮት ያሉ የእጦት ሥዕል እናገኛለን። መዝሙረ ሄላም ላይም እንዲህ ያለ በአንድ ከተማ ላይ የሁለት ምሥሎች አደባባይ እጀግ ብዙ ቦታ ይገኛል።
በሌላኛው የድኅረ-ቅኝ-ግዛት ኂስ (postcolonial criticism) መዝሙረ ሄላምን ስንመለከት መጀመሪያ ላይ “ፈረንጅ ሲያደንቀኝና ሲገረምብኝ የሰሙ የአገሬ ደነዞች በየተራ “ካላስ የኔ ጎሳ ናት” … እያሉ መሻማት ጀመሩ ትላለች - ሄላም። በኋላ ደግሞ በተነዛባት አጓጉል ወሬ … የሄላምን ጡት ንቀው፣ አንጓጥጠው፣ አባረዋት ሲያበቁ የፈረንጅ የዱቄት ወተትን ይመርጣሉ። ይህ በባሕላዊ ማንነትና በዘመናዊነት መካከል የሚዋልል ማኅበረሰብን ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ የድኅረ-ቅኝ-ግዛት አካል ነው። በሌሎቹ የአዳም ሥራዎች ውስጥ ድኅረ-ቅኝ-ግዛት አተያይ በቋንቋና በኪነ-ጥበብ ምርጫ ውስጥ እንዴት እንደሚንፀባረቅ ያሳያል። በመዝሙረ ሄላም ላይ ደግሞ ምዕራባዊው ዓለም ለአገር በቀል መፍትኼ-ሥራይ የሚሰጠው ዋጋ ዝቅተኛ መኾኑንና የኢኮኖሚ ብዝበዛው አሁንም በረቂቅ መንገድ መቀጠሉን ያሳያል። እዚህ ላይ ሥዕለማርያም የተባለችዋን ገጸባሕርይ እና በውጭ ሀገራት የተነዙ ወሬዎችን ስንጨማምር ደግሞ የበለጠ ብዙ ለማለት ያስችላል።
መዝሙረ ሄላም ላይ እጅግ ብዙ ማኅበረሰባዊ ኂስ እናገኛለን። ለአብነት ያህል አንድ ሁለቱን እንቃኝ።
“መዝሙረ ሄላም” ላይ ማኅበረሰቡ በችላ-ባይነት አልያም በኾን ተብሎነት ልጆቹን ምን ያህል ተጠቂ እንዳደረጋቸው የሚያሳይ መልክ ተንጸባርቆበታል ማለት ይቻላል። ጋሽ ክብካብና ዘመናይ ኾን ብለው ቴዲና ሄላም ላይ የሚያደርሱትን፣ ተክለማርያም የወላጁን(የዘሪቱን) ችላ-ባይነት ለአብነት ማቅረብ ይቻላል። ማኅበረሰቡ ልጆችን “የነገ ተስፋዎች” ይላል፤ ነገር ግን ዛሬያቸው ላይ አይሠራም።
ማኅበረሰብ የመማጸኛ ከተማዎችን ወደ ተጨማሪ ግፍ መሥሪያ ቦታዎች እንደሚቀይር በአዳም መጻሕፍት ላይ በብዛት እንመለከታለን። “ይወስዳል መንገድ …” ላይ … “ቀዳዳ” በተሰኘው ታሪክ ላይ ማርታ ለደበበ በምትሰጠው ፍቅር ሳቢያ የሚሠራበትን ግፍ የምታስረሳ ብትኾንም ማኅበረሰቡ ግን ተጨማሪ ግፍ የሚሠራበት መሣሪያ ኾናለች። የስንብት ቀለማት ላይ ምኒልክ ከዚያ ሁሉ እስርና እንግልት በኋላ፣ “በፊያሜታ አርፋለሁ” ብሎ ቤቷ ሲሄድ ተጨማሪ ሕመም በጆሮው በኩል ጭንቅላቱ ላይ ይሻጥበታል። መዝሙረ ሄላም ላይም፣ ሄላም “ሙዚቃዬን ከሕዝብ ጆሮ ያደርስልኛል … ያሳርፈኛል …” ብላ የተመካችበት ምናሴ እንጦሮጦስ ይጨምራታል። ማኅበረሰባችን የመስቀል ተ ሠላጢን ግብር እንዳለው፣ ከላይ አሳልሞ ከታች በአንካሴው ጉድጓድ እንደሚምስ ያሳያል። ይህም የመልእክትን ወጭት ሰብሮ የወጣ ጥበባዊ አጻጻፍ ነው። በፈጣጣው የቀረበ የትችት ኮሶ አይደለም። ድንቅ ነው!
መዝሙረ ሄላም ላይ ከምናገኛቸው ዋና ዋና ገጸባሕርያት የተወሰኑት (አሮን፣ ቃል፣ ምናሴ፣ ሄላም) ላይ መጠነኛ ቅኝት እናድርግ።
auto-fiction ዓይነት አጻጻፍ ባለው የአሮን አተራረክ ውስጥ አሮን “system observer” መኾኑን እንገነዘባለን። ሥርዓቱን ያያል፣ ዘማቹን ያስተውላል፣ ቃለጉባኤ ይይዛል፣ ችግሩን ይመለከታል፣ ይጽፋል። አሮን የተገፋ ታሪክ ድምፅ ነው፤ ንቃት አለው፣ ግን የታሪክ ሂደትን የሚቀይር ኃይል የለውም፤ ስለዚህም ያ ሁሉ የጻፈውን ጽሑፍን ያጣል። የንቃት ችግር የለበትም፤ የማኅበራዊ ንቃት ድምፅነቱን ከዘመነ አባት ጋር ባደረገው ውይይት ውስጥ ተመልክተናል። ግን ደግሞ ይህ ብቻውን የቆመ ነጠላ ነገር ነው፤ ምክንያቱም ማኅበራዊ ተሳትፎ የለበትም። ቃል የተሰኘችው ገጸባሕርይም እንደ አሮን ናት፤ ንቃት ያላት፣ system observer ናት። ማኅበራዊ ንቃት ማኅበራዊ እንቅስቃሴ ካላገዘው ግንጥል ጌጥ ነው። ቃልና አሮን ንቃት አላቸው፤ ግን ንቃታቸውን ተግባር አላገዘውም፤ ንቃቱን የሚተገብር አደረጃጀት የላቸውም። ስለዚህ ዕጣ-ፈንታቸው ውድቀት ይኾናል። በኢትዮጵያ ውስጥ የተንሰራፋውን ይህን የድግግሞሽ አዙሪት መዝሙረ ሄላም ላይ ደራሲ አዳም ረታ በሰላ ብዕር አስቀምጧል።
የደራሲና የአርታኢ ትስስር በተንጸባረቀበት በሄላም አተራረክ ውስጥ ምናሴ የተሰኘ ገጸባሕርይ እናገኛለን። ምናሴ የ-false collective consciousness ትእምርት ነው። ምናሴዎች ለሥልጣን ይሠራሉ፣ ራሳቸውን እንደ ነጻ ያስባሉ፤ ነገር ግን የሥርዓቱ የመጠቀሚያ መሣሪያ (system functionary) ናቸው። ምናሴዎች የኦልቪቴዎች ጥይት ናቸው። ምናሴዎች የሔላምዎች ስኬት ሳይኾን የገዛ ጥቅማቸውን የሚያስቀድሙ የማኅበረሰቡ አካል ናቸው። ምናሴ በሌላ መነጽር ብናየው የመንግሥት ቢሮክራት የመካከለኛው መደብ ውክል ነው። ሀገሩ ከንጉሣዊ ሥርዓት ወደ ወታደራዊ ሥርዓት ቢቀየርም፤ ከወታደራዊ ሥርዓት ወደ ሌላ ሥርዓት ቢለወጥም ምናሴያውያን ግን አይቀየሩም። ሥርዓት ይቀየራል - ምናሴያውያን አይቀየሩም፣ ትእዛዝ ይፈጽማሉ፣ ይከድራሉ። ይህ በኢትዮጵያ ፖለቲካል-ታሪክ ውስጥ የተደጋገመ፣ ግን ደግሞ ያልተስተዋለ እውነት ነው።
ሄላም የወታደር ልጅ ናት፤ እንዲያሳድጋት በአደራ የተሰጠው ቤተሰብ የሚበድላት። የሷ ዓይነት ዕጣ ከደረሰው እንደ ወንድሟ ከምታየው ቴዲ ከሚባል ልጅ ጋር ታድጋለች። መጀመሪያ የሚልዮን፣ የኋላ ኋላ የምናሴ ፍቅረኛ የምትኾን ድምፀ-መረዋ ሴት ናት። ሁሉ ነገሯን ባጣችበት ወቅት ጡቷ ተአምር ያመርታል።
በመዝሙረ ሄላም ላይ የሄላም የጡት ወተት የአንዳች ነገር ውክል ይመስለኛል። ሻዕቢያ ለታጋይ ወጣቶች ማሳደጊያ ፈልጓት ሊሰርቃት መፈለጉ በቀላሉ የሚዘለል ነገር ነው? ወተት እና ጡት በመጀመሪያ እይታ የሕፃናት ትዝታ፣ የእናትነት ምሥል፣ የእምነት እና የጾታ መነሳሳት የተዋሃዱበትም አይደል? ወተት ሕይወት ነው? የመጀመሪያ ምግብ፣ ከእናት ወደ ልጅ የሚፈስም አይደል? በክርስቲያናዊ ምልክት ንጹሕነትን አይወክልም? ወተት ከ“ቅዱስ” ወደ “ሥጋዊ” የሚያስተላልፍ ድልድይ ነው ማለት እንችል ይኾን? የሄላምን ጡት የጠባ ታማሚ ልጅ እንዴት ጤናማ ሊኾን ቻለ? የምን ትእምርት ነው? ሄላም ከብዙ ወንድ ጋር የወጣች እንደመኾኗ ለዚህ ሰናይ ግብር ለምን የሷ ጡት ተመረጠ?
ሌላው፣ መዝሙረ ሄላም ላይ ኦልቬቲን እናገኛታለን። ኦልቬቲ የግራጫ ቃጭልዋ። መዝገቡ ንፋስ መውጫ ሳለ፣ ባልንጀራው ኤልያስ የብልግና ሀሁ ሊያስተምረው እፊቱ ያቆማት ቀይ ሰሌዳ ነበረች ኦልቬቲ። መዝሙረ ሄላም ላይ ምናሴን እና ቤተሰቡን የምታሾር ዐውራ ገጸባሕርይ ኾና ትከሰታለች። መዝሙረ ሄላም እና ግራጫ ቃጭሎች በጋለሞታይቱ በኦልቬቲ ብቻ ሳይኾን በዘመነ እንድርያስ እና በመዝገቡ ዱባለም ይገናኛሉ። ነጋ ዳቦ ጋጋሪውም በ-typological space መዝሙረ ሄላም ላይ እናገኘዋለን።
መዝሙረ ሄላምን ከህላዌነት (Existentialism) አንጻር እንመልከተው። ሄላም ትርጉም በማይሰጥ ዓለም ውስጥ እንዴት እንደምትኖር እናነባለን። የሀገሯ ዳር ድንበር እንዳይነካ አባት ብታዋጣም አሳዳጊዎቿ ግን የወላጅን ፍቅር አዋጥተው አይለግሷትም። ወርቅ አበድራ ጠጠር ትነፈጋለች። ዕቃ ለማገዝ ቤቷ ድረስ ለመጣው ሚልዮን ልቧን ትሰጣለች። ሀና የሸነቆረችውን ክፍተት ለሞላችበት ውለታዋ ክፍያ ይኾን ዘንድ ሚልዮን ለሄላም የወለፈንዴ ቡጢ ያሳርፍባታል። ለሕይወት ትርጉም ለመስጠት ባስ ውስጥ ካገኘችው ሄኖክ ጋር ብትሞክርም የበለጠ የሕይወት ትርጉም ይዛባባታል። የወታደር ልጅ መኾኗ ሄላምነቷን በዜሮ ያባዘዋል። የመጨረሻው ስንብትም ከሄኖክ ጓደኛ አፎት በሚወጣ ሰይፍ መቀላት ይኾናል። ከሄኖክ ጓደኛ ጀርባ የሚውለበለበው ባንዲራ ደግሞ የሄኖክ ሸሚዝ መኾኑ ደግሞ ቁስሉን እንደ አቡሰዲቅ ያደርገዋል። ለሕይወቷ ትልቅ ትርጉም ያለውን የሙዚቃ ሥራዋን፣ “ትርጉም ወዳለው
ነገር ይቀይርልኛል” ብላ በምትተማመንበት በምናሴ ትነጠቃለች። ተአምር በሚያስብለው በጡት ወተት ምክንያት ለሕይወቷ ትርጉም ለመስጠት ትታትራለች። የጡት ወተቷን ምርምር በማድረግ ለትልቅ ዓለምአቀፍ በጎ ተፅዕኖ ታደርጋለች ተብላ የተቆጠረችው ሥዕለማርያም የዓለም አቀፍ መሳለቂያና ትችት ምንጭ ትኾንባታለች። ይህ ሁሉ ትርጉም የሌለው ድግግሞሽ ነው። ይህ ደግሞ በሳርተር የተገለጸውን “existence without essence”-ን ያሳያል።
የህላዌነት መሠረታዊ ሐሳብ ነጻነት ነው፤ ግን ነጻነት ፍርሃትን ይወልዳል። ሄላም ለአሮን ፍቅሯን መናገር ትችላለች፤ ነገር ግን ዝምታን መርጣለች። የግራጫው መዝገቡ፣ የእንጀራ እናቱ የምታደርስበትን በደል እንደሚያውቀው ሁሉ ሄላምም ክብካብና ዘበናይ የሚያደርሱባትን አድሎ ታውቃለች፤ ግን ለረዥም ጊዜ ዝም ብላለች። ሄላም፣ ሙዚቃዋን ካጣች በኋላ ወደ ባንዱ ሄዳ መጋፈጥ ትችላለች፤ ነገር ግን አትሄድም … ይህ በሳርተርኛ bad faith ነው።
የሄላም ምርጫ ዝምታ ኾነ እንጂ ደካማ ናት ማለት አይደለም። “አልተናገርኩም ማለት አላውቀውም ማለት አይደለም” የሚል ዝምታ ነው ያላት። በሌላ ጎኑ ደግሞ ዝምታዋ፣ የለመደችውን ግፍ ከማታውቀው ዐዲስ ግፍ የመምረጥ ኹኔታ ነው። ዐዳዲስ ግፎችን ለመሸሽ በዝምታ አላዋቂነት ዛጎል ውስጥ የመደበቅ ብቃት ነው። የለመደችውን ግፍ የመከላከል አቅም ስላላት ባለመደችው ግፍ እንዳያጠፏት ሠግታ በውስጣዊ ንቃተ ሕሊና የዘየደችው ብልሃት ሊኾን ይችላል። ዝምታዋ የመቆየቷ ምሥጢር ነው። ደበበ ቀዝቃዛ ገለልተኛ ነኝ የሚለው ሰው ለመኖር ሲል ሳይታወቀው ስሜቱን የሚቆጣጠርበት መንገድን ለማስታወስ ነው።
“የስንብት ቀለማት” ገጸባሕርይ የኾነው ዮሴፍም ብዙ ነገር ያውቃል፤ ግን ዝም ይላል … ፊያሜታ ቂል መስሏት ትዘባርቃለች … እሱ ግን “አልተናገርኩም ማለት አላውቀውም ማለት አይደለም” የሚል የዝምታ መልስ ይመልስላታል። እሷ ግን ዝምታው አይገባትም። የ“ቀዳዳ”ው ደበበ እና “የስንብት …” ዮሴፍ ቀዳዳውን አይሞሉትም፤ እያዩት ይኖራሉ። ዶነሮች ጥሩ ፈንድ ሲለቁ ፊያሜታ ፕሮጀክቱን ለአሳምነው ትሰጠውና ዮሴፍን “ምን ዶነሮች እኮ ጠፉ ትለዋለች” … ዝም ይላል፤ ይታዘባል።
ቃል መሣሪያ ነበር፤ በዘመነ ደበበ፣ በዘመነ ዮሴፍ፣ በዘመነ ሄላም እና በዘመነ መዝገቡ ዱባለ ግን ቃል አደገኛ ኾኗል፤ ዝምታ ኹነኛ መጠጊያ ነው … ይህ ከደርግ በኋላ የተፈጠረ “traumatized literary silence” ማሳያ ነው። ስለኾነም ተራኪዎቹ (ደበበ፣ መዝገቡ፣ ዮሴፍ እና ሄላም) ለምን ዝም አሉ ሳይኾን "ዝምታን የሚያመነጭ ሥርዓት ምን ይኾን?" ብለን እንድንጠይቅ ያደርጋል። ግለሰብ ዝም ሲል፤ ሕዝብ በጸጥታ ይዋጣል፤ የዚያኔ የተማከለው ኃይል አፍ ያወጣል።
የአዳምን ዐዲሱን መጽሐፍ "በንባብ ይለቅ" ብለን መርቀናል።
ቢኒያም አቡራ
ሐምሌ 25 / 2018 ዓ.ም
ከቢኒያም አቡራ
#ethiopia | አዳም ረታ ታሪክን ከነገሥታት፣ ከመሪዎች፣ ማኅበረሰቡ ባበጀው ድልድል ውስጥ ‹ላዕላይ› ከሚባሉት ደረጃዎች አንጻር አያስመለክተንም። ታሪካዊ ከሚባሉ አጋጣሚዎች ውስጥ የተዘነጉትን ጥቃቅን የታሪክ ኹነተ-ደቂቅ (micro-events) ይመርጣል። ይወስዳል መንገድ ላይ … “ቀዳዳ” በተሰኘው ታሪክ ላይ ፍንዳታውን ከሚሞት ዘመድ፣ ከሚደነግጥ ለማኝ፣ ከሚሰነጠቅ የወፍ እንቁላል፣ ከሚፈስ የእናት ወተት ጋር Micro-Macro Connection በመፍጠር የትልቁ ቀዳዳ መፈጠርን ከሚጢጢዬ ሽንቁሮች ጋር ያስተሳስርልናል። እንዲህ ያሉ የኒው ሂስቶሪሲዝም ባሕሪያትን ከዚህ ቀደም ባሳተማቸው መጻሕፍቱ ውስጥ በተለያየ መጠን እናገኛለን።
Adam Reta አዳም ረታ "መዝሙረ ሄላም" በተሰኘው በዐዲሱ መጽሐፉ ላይም በኢትዮጵያ ታሪካዊ-ፖለቲካዊ አጋጣሚ ውስጥ እንደ ዐውራ የሚታዩትን የእድገት በኅብረት ዘመቻን እንደነ-አሮን፣ እንደነቃል … ባሉ ገጸባሕርያት በኩል፣ የሰባ ሰባቱን ድርቅ በሄላም ጡት በኩል፣ “ጥላሁን ለምን ለምን ሞተ” እየተባለ ኢዮቤልዩ ቤተመንግሥት ጋር የተደረገውን ሰላማዊ ሰልፍ በሡልጣን በኩል፣ የከተማ መሬት ዐዋጅን በተለያዩ ግለሰቦች በኩል … እናያለን። በዚህም የታሪክን ትልቅ ካርታ ለመረዳት የተረሱና የጠለሉ ታሪኮችን ይመረምራል። ስለዚህ ነቁጣዊ ማኅበራዊ ክስተቶችን ወደ ታሪክ ምኩራብ በማምጣት ከትልቁ የታሪክ ምሥል ጎን ያስተያያል። ይህ ደግሞ የኒው ሂስቶሪሲዝም ኹነኛ ማጠንጠኛ ነው።
ልክ “ይወስዳል መንገድ ያመጣል መንገድ …” በተሰኘው መጽሐፉ ውስጥ ባለው “የመንግሥቱ ጊዜ” በሚለው ድርሰት ውስጥ፣ ትልቁን “የታኅሣሥ ግርግር”ን እንደ መቼት አምጥቶ የተጻፈውና የተተኮረው ግን ኹነተ-ደቂቅ (micro-events) ላይ ነው። ስለግርማሜ ንዋይ፣ ስለኮሌኔል ወርቅነህ ገበየሁ፣ ሰለጄነራል ሙልጌታ ቡሊ አይደለም የሚያትተው። ስለአንድ ብላቴና ከእንቅልፍ መነሳት፣ ስለገበጣ ጨዋታ፣ ቤተክርስቲያን ውስጥ ሕፃናትን አሰብስቦ ‹ኪራላይሶን› የሚያስብል ካሕን፣ ስለመንደር ውስጥ ሐሜቶች፣ ስለግለሰቦች ፍርሃት፣ በአጋጣሚ ስላየው አስደናቂ አሞራ … ያወጋል። የታሪክ አጋጣሚ አምጥቶ በታሪክ ውስጥ ግለሰቦች ላይ ስለሚረብበው የታሪክ መንፈስ ያትታል። ልክ እንደዚሁ መዝሙረ ሄላም ላይም ጽሑፉ ታሪክን አያብራራም፤ ነገር ግን ታሪክ እንዴት በሰው ልብ ውስጥ እንደሚኖር ያሳያል። በዚህ ኹነተ-ደቂቅ (micro-event) ምክንያት በዘመኑ ላይ ያገነገነውን ባሕላዊ እምነትን፣ የሥልጣን መዋቅርን፣ የወል ግንዛቤን አጨንቁረን እንድንመለከት ያስችለናል።
ከመንግሥት ሼልፍ ላይ ሳይኾን ከግለሰብ ጀርባ ላይ የተወሰደው የአዳም የአጻጻፍ መንገድ ከኒው ሂስቶሪስዝም ጽንሰ-ሐሳቦች ጋር በአንድ መም ላይ የሚሄዱ ናቸው። መዝሙረ ሄላም የተሰኘው ዐዲሱ የአዳም ረታ መጽሐፍ የኒው ሂስቶሪሲዝም ባሕርያትን ይጋራል። አንዳንድ ነገሮችን በዓይን መመልከት ባይቻልም በግብሩ (ቁስ ላይ በሚያደርገው ግፊት) ግን ይታወቃል። በመዝሙረ ሄላም መጽሐፍ ውስጥም አንዳንድ ነገሮችን በቀጥታ ማየት ባንችልም ቅሉ እነርሱን የሚያሳይልንን ነገሮች ግን እንቃኛለን። ዘማች ወጣት ተማሪዎችን እናያለን፤ መንግሥትን፣ ሕግንና ኃይልን ግን በቀጥታ አንመለከትም። የተማከለ ኃይል አናይም ግን የገጸባሕርያቱ የፍርሃት ምንጭ ከተማከለ ኃይል ጋር የተያያዘ ቀጭን መስመር መኖሩን እናያለን። መንግሥትም ቢኾን በቀጥታ አይገባም፤ ነገር ግን ፍርሃት እንደ ሥርዓት ዘዋሪ (system driver) ይኾናል። እንደ ሚሸል ፉኮ አገላለጽ ኃይል ከተማከለ ሥርዓት የሚመነጭ ሳይኾን በየትኛውም ቦታና ጊዜ በፍርሃት፣ በልማድ፣ በንግግር … ሊከሰት የሚችል ሂደት አይደል?
መዝሙረ ሄላም ላይ ታሪክ እንደ “circulation of social energy” ቀርቧል። መዝሙረ ሄላም ላይ መረጃ ከመንግሥት አይመጣም፤ ከግለሰብ እንጂ። የከተማ መሬት ዐዋጅም ኾነ የተማሪዎች ዘመቻ በገጸባሕርያቱ ወሬ ውስጥ ነው የሚንቀረቀበው። ይህ የመረጃ ሥርዓት ኃይል ማን እንዳለው ማን እንደሌለው ያሳያል። እንግዲህ ይህ በፉኮኛ micro-power መኾኑ ነው። በመዝሙረ ሄላም ላይ ታሪክ እንደ ወሬ እንጂ እንደ ሰነድ አይቀርብም።
ወሬ የፍርሃት ቤንዚን ነው … ፍርሃት ደግሞ በዝምታ መሸበብን ይፈጥራል … የዝምታ አፈ-ሙቅ ደግሞ ኃይለኛው እንዳይታይ ያደርጋል … የተደራጀው ኃይል ጥፋትን ሊያደርስ ባሰበ ቁጥር የወሬ ቤንዚን ይጨምራል። ሰዎች በዕቅብተ-ንግግር ራሳቸውን ሲሸብቡ ደርዝ ያለው ሙግት ይኮሰምናል፣ ንግግር ሲጠፋ ያልታወቀ አደጋ ይከሰታል፣ ፍርሃትም ይጨምራል። ያልታወቀ አደጋ ደግሞ ከታወቀ አካል ይመጣል። ስለዚህ ጥንስሱ የሚጀምረው ከወሬ እንደኾነ ያስመለክተናል። አዳም በመዝሙረ ሄላም ላይ ታሪክን እንደ “circulation of social energy” ሲያቀርብ ፕሬዝዳንት፣ ጀነራል፣ ፕሮፌሰር የኾኑ ታሪክ ከላዕላይ ያስቀመጣቸው ሰዎች አያስፈልጉትም። በአንጻሩ ሄላም ለማን እንደሳመችው ተደርጎ ብርሃኔ ያስወራው ወሬ፣ የሄላም አባት ወታደር በመኾኑ ምክንያት በካሱ፣ በሄኖክ እናት የተነዛው ወሬ እና ሄላም ከሄኖክ ጋር የተቆራረጠችበት መንገድ እንዲሁም የሄላምን የጡት ወተት በተመለከተ የተነዛው ወሬን ይጠቀማል።
መዝሙረ ሄላምን ከድኅረ-ቅኝ-አገዛዝ የኂስ መንገድ አንጻር እንመልከተው።
እውን ቅኝ-ግዛት ተረት ኾኖ ቀርቷል? በፖለቲካ፣ በኢኮኖሚ፣ በሥነልቦና ረገድ የቅኝ አገዛዝ ዳናው ሙሉ ለሙሉ ጠፍቷል? አዳም በመዝሙረ ሄላም ጽሑፍ ውስጥ ከቅኝ-ግዛት በተወረሰ መዋቅር ምክንያት የተሰናከለን ሕይወት ሊያስመለክተን ይኾን?
“ከተሞች ከቅኝ ግዛት በኋላ ሁለት ዓይነት መልክ ይኖራቸዋል፤ ለጥቂቱ የተድላ፣ ለተቀረው ደግሞ የአሳር መንደር ይኾናሉ” ይላል ፍራንዝ ፋኖን። በመዝሙረ ሄላም ላይ እና “የቢሾፍቱ ልጆች ጥላሞት” የተሰኘው ድርሰት ላይም ይህንን ነው የምንመለከተው። “ይወስዳል መንገድ ያመጣል መንገድ …” በተሰኘው መጽሐፉ ውስጥ ካሉ ጽሑፎች መካከል “የቢሾፍቱ ልጆች ጥላ ሞት” አንዱ ነው። የቢሾፍቱ ልጆች ሆቴሉን ያዩታል፤ ግን አይገቡበትም። ሆቴሉ የሀገራቸው መሬት ላይ ነው፤ እነርሱ ግን ከሆቴሉ ውጭ ናቸው። መናፈሻው ውስጥ አንዲት የፈረንጅ ልጅ ጠግባ ለልጆቹ እንደ ውሻ ዳቦ ትወረውርላቸዋለች። አፈር ላይ የወደቀን ዳቦ አራግፈው ይመገባሉ። በገዛ ሐይቃቸው ዳር ላይ ናቸው፤ ሌሎች ግን በጀልባ እየተንሸራሸሩ ይንፈላሰሳሉ። ለፈረንጆቹ ያደረው ሞገስ የላንድሮቨር ተፈናጣጭ ኾኗል። ሌሎቹ ግን ከመኪናው ውጪ ናቸው። ሞገስ እንደ እነርሱ ሕጻን ቢኾንም ለፈረንጅ በማሸርገዱ የትምህርት ቤቱ ባለቤት ሲመስል ሌሎች ልጆች ግን በገዛ መምህራቸው ይብጠለጠላሉ። የቢሾፍቱ ልጆች፣ ነጻ በተባለች ሀገር እየኖሩ በቅኝ ግዛት ጥላ ይተዳደራሉ። የቢሾፍቱ ልጆች በገዛ መንደራቸው አካሉ በማይታይ የቅኝ ግዛት እጅ ይገፋሉ። ሞገስ አይናገርም፤ የሚናገርለት አለ። ልክ የቢሾፍቱ ልጆች ላይ በአንድ ከተማ ውስጥ ሁለት የከተማ ምሥል እንደምናገኘው ሁሉ “የስንብት ቀለማት” ላይም በአዲስ አበባ ውስጥ ሁለት የከተማ ምሥል እንመለከታለን። እንደ ዘድሬክ፣ ሳተርን፣ ከተስፋዬ ወደ አሸናፊ የተቀየሩ የድሎት ምሥሎች እና የእነምትክ ጉልት፣ የእትየ እልልታ የጉርሻ መሸጫ መስኮት ያሉ የእጦት ሥዕል እናገኛለን። መዝሙረ ሄላም ላይም እንዲህ ያለ በአንድ ከተማ ላይ የሁለት ምሥሎች አደባባይ እጀግ ብዙ ቦታ ይገኛል።
በሌላኛው የድኅረ-ቅኝ-ግዛት ኂስ (postcolonial criticism) መዝሙረ ሄላምን ስንመለከት መጀመሪያ ላይ “ፈረንጅ ሲያደንቀኝና ሲገረምብኝ የሰሙ የአገሬ ደነዞች በየተራ “ካላስ የኔ ጎሳ ናት” … እያሉ መሻማት ጀመሩ ትላለች - ሄላም። በኋላ ደግሞ በተነዛባት አጓጉል ወሬ … የሄላምን ጡት ንቀው፣ አንጓጥጠው፣ አባረዋት ሲያበቁ የፈረንጅ የዱቄት ወተትን ይመርጣሉ። ይህ በባሕላዊ ማንነትና በዘመናዊነት መካከል የሚዋልል ማኅበረሰብን ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ የድኅረ-ቅኝ-ግዛት አካል ነው። በሌሎቹ የአዳም ሥራዎች ውስጥ ድኅረ-ቅኝ-ግዛት አተያይ በቋንቋና በኪነ-ጥበብ ምርጫ ውስጥ እንዴት እንደሚንፀባረቅ ያሳያል። በመዝሙረ ሄላም ላይ ደግሞ ምዕራባዊው ዓለም ለአገር በቀል መፍትኼ-ሥራይ የሚሰጠው ዋጋ ዝቅተኛ መኾኑንና የኢኮኖሚ ብዝበዛው አሁንም በረቂቅ መንገድ መቀጠሉን ያሳያል። እዚህ ላይ ሥዕለማርያም የተባለችዋን ገጸባሕርይ እና በውጭ ሀገራት የተነዙ ወሬዎችን ስንጨማምር ደግሞ የበለጠ ብዙ ለማለት ያስችላል።
መዝሙረ ሄላም ላይ እጅግ ብዙ ማኅበረሰባዊ ኂስ እናገኛለን። ለአብነት ያህል አንድ ሁለቱን እንቃኝ።
“መዝሙረ ሄላም” ላይ ማኅበረሰቡ በችላ-ባይነት አልያም በኾን ተብሎነት ልጆቹን ምን ያህል ተጠቂ እንዳደረጋቸው የሚያሳይ መልክ ተንጸባርቆበታል ማለት ይቻላል። ጋሽ ክብካብና ዘመናይ ኾን ብለው ቴዲና ሄላም ላይ የሚያደርሱትን፣ ተክለማርያም የወላጁን(የዘሪቱን) ችላ-ባይነት ለአብነት ማቅረብ ይቻላል። ማኅበረሰቡ ልጆችን “የነገ ተስፋዎች” ይላል፤ ነገር ግን ዛሬያቸው ላይ አይሠራም።
ማኅበረሰብ የመማጸኛ ከተማዎችን ወደ ተጨማሪ ግፍ መሥሪያ ቦታዎች እንደሚቀይር በአዳም መጻሕፍት ላይ በብዛት እንመለከታለን። “ይወስዳል መንገድ …” ላይ … “ቀዳዳ” በተሰኘው ታሪክ ላይ ማርታ ለደበበ በምትሰጠው ፍቅር ሳቢያ የሚሠራበትን ግፍ የምታስረሳ ብትኾንም ማኅበረሰቡ ግን ተጨማሪ ግፍ የሚሠራበት መሣሪያ ኾናለች። የስንብት ቀለማት ላይ ምኒልክ ከዚያ ሁሉ እስርና እንግልት በኋላ፣ “በፊያሜታ አርፋለሁ” ብሎ ቤቷ ሲሄድ ተጨማሪ ሕመም በጆሮው በኩል ጭንቅላቱ ላይ ይሻጥበታል። መዝሙረ ሄላም ላይም፣ ሄላም “ሙዚቃዬን ከሕዝብ ጆሮ ያደርስልኛል … ያሳርፈኛል …” ብላ የተመካችበት ምናሴ እንጦሮጦስ ይጨምራታል። ማኅበረሰባችን የመስቀል ተ ሠላጢን ግብር እንዳለው፣ ከላይ አሳልሞ ከታች በአንካሴው ጉድጓድ እንደሚምስ ያሳያል። ይህም የመልእክትን ወጭት ሰብሮ የወጣ ጥበባዊ አጻጻፍ ነው። በፈጣጣው የቀረበ የትችት ኮሶ አይደለም። ድንቅ ነው!
መዝሙረ ሄላም ላይ ከምናገኛቸው ዋና ዋና ገጸባሕርያት የተወሰኑት (አሮን፣ ቃል፣ ምናሴ፣ ሄላም) ላይ መጠነኛ ቅኝት እናድርግ።
auto-fiction ዓይነት አጻጻፍ ባለው የአሮን አተራረክ ውስጥ አሮን “system observer” መኾኑን እንገነዘባለን። ሥርዓቱን ያያል፣ ዘማቹን ያስተውላል፣ ቃለጉባኤ ይይዛል፣ ችግሩን ይመለከታል፣ ይጽፋል። አሮን የተገፋ ታሪክ ድምፅ ነው፤ ንቃት አለው፣ ግን የታሪክ ሂደትን የሚቀይር ኃይል የለውም፤ ስለዚህም ያ ሁሉ የጻፈውን ጽሑፍን ያጣል። የንቃት ችግር የለበትም፤ የማኅበራዊ ንቃት ድምፅነቱን ከዘመነ አባት ጋር ባደረገው ውይይት ውስጥ ተመልክተናል። ግን ደግሞ ይህ ብቻውን የቆመ ነጠላ ነገር ነው፤ ምክንያቱም ማኅበራዊ ተሳትፎ የለበትም። ቃል የተሰኘችው ገጸባሕርይም እንደ አሮን ናት፤ ንቃት ያላት፣ system observer ናት። ማኅበራዊ ንቃት ማኅበራዊ እንቅስቃሴ ካላገዘው ግንጥል ጌጥ ነው። ቃልና አሮን ንቃት አላቸው፤ ግን ንቃታቸውን ተግባር አላገዘውም፤ ንቃቱን የሚተገብር አደረጃጀት የላቸውም። ስለዚህ ዕጣ-ፈንታቸው ውድቀት ይኾናል። በኢትዮጵያ ውስጥ የተንሰራፋውን ይህን የድግግሞሽ አዙሪት መዝሙረ ሄላም ላይ ደራሲ አዳም ረታ በሰላ ብዕር አስቀምጧል።
የደራሲና የአርታኢ ትስስር በተንጸባረቀበት በሄላም አተራረክ ውስጥ ምናሴ የተሰኘ ገጸባሕርይ እናገኛለን። ምናሴ የ-false collective consciousness ትእምርት ነው። ምናሴዎች ለሥልጣን ይሠራሉ፣ ራሳቸውን እንደ ነጻ ያስባሉ፤ ነገር ግን የሥርዓቱ የመጠቀሚያ መሣሪያ (system functionary) ናቸው። ምናሴዎች የኦልቪቴዎች ጥይት ናቸው። ምናሴዎች የሔላምዎች ስኬት ሳይኾን የገዛ ጥቅማቸውን የሚያስቀድሙ የማኅበረሰቡ አካል ናቸው። ምናሴ በሌላ መነጽር ብናየው የመንግሥት ቢሮክራት የመካከለኛው መደብ ውክል ነው። ሀገሩ ከንጉሣዊ ሥርዓት ወደ ወታደራዊ ሥርዓት ቢቀየርም፤ ከወታደራዊ ሥርዓት ወደ ሌላ ሥርዓት ቢለወጥም ምናሴያውያን ግን አይቀየሩም። ሥርዓት ይቀየራል - ምናሴያውያን አይቀየሩም፣ ትእዛዝ ይፈጽማሉ፣ ይከድራሉ። ይህ በኢትዮጵያ ፖለቲካል-ታሪክ ውስጥ የተደጋገመ፣ ግን ደግሞ ያልተስተዋለ እውነት ነው።
ሄላም የወታደር ልጅ ናት፤ እንዲያሳድጋት በአደራ የተሰጠው ቤተሰብ የሚበድላት። የሷ ዓይነት ዕጣ ከደረሰው እንደ ወንድሟ ከምታየው ቴዲ ከሚባል ልጅ ጋር ታድጋለች። መጀመሪያ የሚልዮን፣ የኋላ ኋላ የምናሴ ፍቅረኛ የምትኾን ድምፀ-መረዋ ሴት ናት። ሁሉ ነገሯን ባጣችበት ወቅት ጡቷ ተአምር ያመርታል።
በመዝሙረ ሄላም ላይ የሄላም የጡት ወተት የአንዳች ነገር ውክል ይመስለኛል። ሻዕቢያ ለታጋይ ወጣቶች ማሳደጊያ ፈልጓት ሊሰርቃት መፈለጉ በቀላሉ የሚዘለል ነገር ነው? ወተት እና ጡት በመጀመሪያ እይታ የሕፃናት ትዝታ፣ የእናትነት ምሥል፣ የእምነት እና የጾታ መነሳሳት የተዋሃዱበትም አይደል? ወተት ሕይወት ነው? የመጀመሪያ ምግብ፣ ከእናት ወደ ልጅ የሚፈስም አይደል? በክርስቲያናዊ ምልክት ንጹሕነትን አይወክልም? ወተት ከ“ቅዱስ” ወደ “ሥጋዊ” የሚያስተላልፍ ድልድይ ነው ማለት እንችል ይኾን? የሄላምን ጡት የጠባ ታማሚ ልጅ እንዴት ጤናማ ሊኾን ቻለ? የምን ትእምርት ነው? ሄላም ከብዙ ወንድ ጋር የወጣች እንደመኾኗ ለዚህ ሰናይ ግብር ለምን የሷ ጡት ተመረጠ?
ሌላው፣ መዝሙረ ሄላም ላይ ኦልቬቲን እናገኛታለን። ኦልቬቲ የግራጫ ቃጭልዋ። መዝገቡ ንፋስ መውጫ ሳለ፣ ባልንጀራው ኤልያስ የብልግና ሀሁ ሊያስተምረው እፊቱ ያቆማት ቀይ ሰሌዳ ነበረች ኦልቬቲ። መዝሙረ ሄላም ላይ ምናሴን እና ቤተሰቡን የምታሾር ዐውራ ገጸባሕርይ ኾና ትከሰታለች። መዝሙረ ሄላም እና ግራጫ ቃጭሎች በጋለሞታይቱ በኦልቬቲ ብቻ ሳይኾን በዘመነ እንድርያስ እና በመዝገቡ ዱባለም ይገናኛሉ። ነጋ ዳቦ ጋጋሪውም በ-typological space መዝሙረ ሄላም ላይ እናገኘዋለን።
መዝሙረ ሄላምን ከህላዌነት (Existentialism) አንጻር እንመልከተው። ሄላም ትርጉም በማይሰጥ ዓለም ውስጥ እንዴት እንደምትኖር እናነባለን። የሀገሯ ዳር ድንበር እንዳይነካ አባት ብታዋጣም አሳዳጊዎቿ ግን የወላጅን ፍቅር አዋጥተው አይለግሷትም። ወርቅ አበድራ ጠጠር ትነፈጋለች። ዕቃ ለማገዝ ቤቷ ድረስ ለመጣው ሚልዮን ልቧን ትሰጣለች። ሀና የሸነቆረችውን ክፍተት ለሞላችበት ውለታዋ ክፍያ ይኾን ዘንድ ሚልዮን ለሄላም የወለፈንዴ ቡጢ ያሳርፍባታል። ለሕይወት ትርጉም ለመስጠት ባስ ውስጥ ካገኘችው ሄኖክ ጋር ብትሞክርም የበለጠ የሕይወት ትርጉም ይዛባባታል። የወታደር ልጅ መኾኗ ሄላምነቷን በዜሮ ያባዘዋል። የመጨረሻው ስንብትም ከሄኖክ ጓደኛ አፎት በሚወጣ ሰይፍ መቀላት ይኾናል። ከሄኖክ ጓደኛ ጀርባ የሚውለበለበው ባንዲራ ደግሞ የሄኖክ ሸሚዝ መኾኑ ደግሞ ቁስሉን እንደ አቡሰዲቅ ያደርገዋል። ለሕይወቷ ትልቅ ትርጉም ያለውን የሙዚቃ ሥራዋን፣ “ትርጉም ወዳለው
ነገር ይቀይርልኛል” ብላ በምትተማመንበት በምናሴ ትነጠቃለች። ተአምር በሚያስብለው በጡት ወተት ምክንያት ለሕይወቷ ትርጉም ለመስጠት ትታትራለች። የጡት ወተቷን ምርምር በማድረግ ለትልቅ ዓለምአቀፍ በጎ ተፅዕኖ ታደርጋለች ተብላ የተቆጠረችው ሥዕለማርያም የዓለም አቀፍ መሳለቂያና ትችት ምንጭ ትኾንባታለች። ይህ ሁሉ ትርጉም የሌለው ድግግሞሽ ነው። ይህ ደግሞ በሳርተር የተገለጸውን “existence without essence”-ን ያሳያል።
የህላዌነት መሠረታዊ ሐሳብ ነጻነት ነው፤ ግን ነጻነት ፍርሃትን ይወልዳል። ሄላም ለአሮን ፍቅሯን መናገር ትችላለች፤ ነገር ግን ዝምታን መርጣለች። የግራጫው መዝገቡ፣ የእንጀራ እናቱ የምታደርስበትን በደል እንደሚያውቀው ሁሉ ሄላምም ክብካብና ዘበናይ የሚያደርሱባትን አድሎ ታውቃለች፤ ግን ለረዥም ጊዜ ዝም ብላለች። ሄላም፣ ሙዚቃዋን ካጣች በኋላ ወደ ባንዱ ሄዳ መጋፈጥ ትችላለች፤ ነገር ግን አትሄድም … ይህ በሳርተርኛ bad faith ነው።
የሄላም ምርጫ ዝምታ ኾነ እንጂ ደካማ ናት ማለት አይደለም። “አልተናገርኩም ማለት አላውቀውም ማለት አይደለም” የሚል ዝምታ ነው ያላት። በሌላ ጎኑ ደግሞ ዝምታዋ፣ የለመደችውን ግፍ ከማታውቀው ዐዲስ ግፍ የመምረጥ ኹኔታ ነው። ዐዳዲስ ግፎችን ለመሸሽ በዝምታ አላዋቂነት ዛጎል ውስጥ የመደበቅ ብቃት ነው። የለመደችውን ግፍ የመከላከል አቅም ስላላት ባለመደችው ግፍ እንዳያጠፏት ሠግታ በውስጣዊ ንቃተ ሕሊና የዘየደችው ብልሃት ሊኾን ይችላል። ዝምታዋ የመቆየቷ ምሥጢር ነው። ደበበ ቀዝቃዛ ገለልተኛ ነኝ የሚለው ሰው ለመኖር ሲል ሳይታወቀው ስሜቱን የሚቆጣጠርበት መንገድን ለማስታወስ ነው።
“የስንብት ቀለማት” ገጸባሕርይ የኾነው ዮሴፍም ብዙ ነገር ያውቃል፤ ግን ዝም ይላል … ፊያሜታ ቂል መስሏት ትዘባርቃለች … እሱ ግን “አልተናገርኩም ማለት አላውቀውም ማለት አይደለም” የሚል የዝምታ መልስ ይመልስላታል። እሷ ግን ዝምታው አይገባትም። የ“ቀዳዳ”ው ደበበ እና “የስንብት …” ዮሴፍ ቀዳዳውን አይሞሉትም፤ እያዩት ይኖራሉ። ዶነሮች ጥሩ ፈንድ ሲለቁ ፊያሜታ ፕሮጀክቱን ለአሳምነው ትሰጠውና ዮሴፍን “ምን ዶነሮች እኮ ጠፉ ትለዋለች” … ዝም ይላል፤ ይታዘባል።
ቃል መሣሪያ ነበር፤ በዘመነ ደበበ፣ በዘመነ ዮሴፍ፣ በዘመነ ሄላም እና በዘመነ መዝገቡ ዱባለ ግን ቃል አደገኛ ኾኗል፤ ዝምታ ኹነኛ መጠጊያ ነው … ይህ ከደርግ በኋላ የተፈጠረ “traumatized literary silence” ማሳያ ነው። ስለኾነም ተራኪዎቹ (ደበበ፣ መዝገቡ፣ ዮሴፍ እና ሄላም) ለምን ዝም አሉ ሳይኾን "ዝምታን የሚያመነጭ ሥርዓት ምን ይኾን?" ብለን እንድንጠይቅ ያደርጋል። ግለሰብ ዝም ሲል፤ ሕዝብ በጸጥታ ይዋጣል፤ የዚያኔ የተማከለው ኃይል አፍ ያወጣል።
የአዳምን ዐዲሱን መጽሐፍ "በንባብ ይለቅ" ብለን መርቀናል።
ቢኒያም አቡራ
ሐምሌ 25 / 2018 ዓ.ም
Sponsored by
Surafel
2 days ago
ኢትዮ-ኢስታንቡል ሆስፒታል በዓመት ከ79 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች ህክምና መስጠቱን ገለጸ
ኢትዮ-ኢስታንቡል ጠቅላላ ሆስፒታል በተመሰረተ በአጭር ጊዜ ወደውጭ ሀገር በሚወስዱ የህክምና ጥገኝነትን በመቀየር፣ በሀገር ውስጥ ዘመናዊ ህክምና መስጠት የሚያስችል አገልግሎት መዘርጋቱን አስታወቀ።
ኢትዮ-ኢስታንቡል አጠቃላይ ሆስፒታል ሐምሌ 28 ቀን 2018 ዓ.ም ለመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች በሰጠው መግለጫ ላይ እንደተገለጸው ሆስፒታሉ በመሥራቹና ባለራዕዩ ሲኢኦ አቶ ብርሃን ተድላ እየተመራ ከተመሰረተበት ጊዜ ጀምሮ ለታካሚዎች ጥራቱን የጠበቀ የሕክምና አገልግሎት ሲሰጥ የቆየ ሲሆን፣ በተለይም በያዝነው 2018 ዓ.ም ብቻ ከ79 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የተመላላሽ ህክምና አገልግሎት በመስጠትና ከ4 ሺ 500 በላይ የቀዶ ህክምናዎችን በማካሄድ አመርቂ ውጤት አስመዝግቧል።
ሆስፒታሉ እነዚህን ሀገር በቀል አቅሞች በመገንባቱ ቀደም ሲል ለህክምና ወደ ውጭ ሀገር ይሄዱ የነበሩ ታካሚዎችን ቁጥር በመቀነስ የውጭ ምንዛሬን ከማስቀረት ባሻገር የታካሚዎችን ችግር መቅረፍ ችሏል።
በመግለጫው ወቅት የሆስፒታሉ ሜዲካል ዳይሬክተር፣ የአጠቃላይ እና ደረት አካባቢ ቀዶ ህክምና ስፔሻሊስት ተባባሪ ኘሮፌሰር ስዩም ካሣ መርኔ እንደገለጹት፣ ተቋሙ በኢንተርቬንሽናል ካርዲዮሎጂ መስክ ያለ ኦፕሬሽን በደም ስሮች በኩል በሚደረግ ህክምና ጨምሮ በአዋቂና በልጆች የልብ ሕክምና በአጠቃላይ ከ735 በላይ ታካሚዎችን መታደግ ችሏል። አክለውም ይህ አገልግሎት ዓመቱን ሙሉ ሌሊትና ቀን ሳይቋረጥ የሚሰጥ በመሆኑ፣ ከውጭ ሀገር በሚመጡ ጊዜያዊ ዘመቻዎች ላይ ብቻ ጥገኛ የነበረውን አሰራር መቀየር መቻሉን ገልጸዋል።
ሆስፒታሉ በኢትዮጵያውያን ባለሙያዎች በመታገዝ ወደውጪ ሀገር የሚያስኬዱ በተለይ የልብ ሕክምናዎችን 90 በመቶ በሆስፒታሉ መስጠት መቻሉን ጠቅሰዋል።
እንደ ዶክተር ስዩም ገለጻ፣ ሆስፒታሉ በኒውሮሰርጀሪ፣ በኦፕን ካርዲያክ፣ በአጥንትና ስፓይን፣ በኩላሊት፣ በሳምባ፣ የአንጎል፣ የዳሌና የጉልበት ቅየራ እንዲሁም በሚኒማሊ ኢንቬሲቭ (ላፓሮስኮፒክና ቶራኮስኮፒክ) እና ከ46 በላይ ሰብስፔሻሊቲ ህክምና ዘርፎች የላቀ አገልግሎት እየሰጠ ሲሆን፣ የሬዲዮሎጂ ክፍሉም የሰው ሰራሽ አስተውሎት ቴክኖሎጂን በመጠቀም የህክምና ምርመራ ጥራቱን በማሳደግ ላይ ይገኛል ብለዋል።
የሆስፒታሉ የውስጥ ደዌና የአዋቂዎች ኢንተርቬንሽናል የልብ ህክምና ስፔሻሊስት ዶክተር ከፈለኝ ደጀኔ በበኩላቸው እንደገለጹት፣ ከተሰሩት 321 የሕፃናት የልብ ህክምናዎች መከናወናቸውን ጠቁመው 90 የሚጠጋ ድንገተኛ የልብ ደምስር መዘጋት አደጋ ያጋጠማቸውና ታካሚዎች በ24 ሰዓት ድንገተኛ አደጋዎች አገልግሎት ህይወታቸው መታደግ ተችላል ብለዋል። ከእነዚህም ውስጥ ቁጥራቸው ከ90 በላይ የሚኾኑ የውጭ ሀገር ዜጎችና ዲፕሎማቶች እንዲሁም ነፍሰጡር እናቶች ይገኙበታል።
የሆስፒታሉ የቺፍ ኦፕሬሽንስ ዳይሬክተር፣ የአንገትና ጭንቅላት ሰብ-ስፔሻሊስት ዶክተር መለስ ገበየሁ እንደገለጹት ደግሞ፣ ተቋሙ ከንግድ ዓላማው ጎን ለጎን ማህበራዊ ኃላፊነቱን በመወጣት ረገድ ትልቅ ስራ እየሰራ ይገኛል። በሆስፒታሉ ባለቤትና ዋና ስራአስፈጻሚ አቶ ብርሃን ተድላ አማካይነት በተቋቋመው "Heart to Heart Children's Aid" የተሰኘ ፋውንዴሽን በኩል ትልቅ ሥራዎች መከናወናቸውን አስታውሰዋል።
ሜዲካል ዳይሬክተሩ በመጨረሻም ኢትዮ ኢስታንቡል ጠቅላላ ሆስፒታል በሰኔ ወር 2015 ዓ.ም ጀምሮ ወደሥራ መግባቱና በአጭር ጊዜ ውስጥ ከፍተኛ ውጤት መድረስ የቻለው በተቋሙ መስራችና ሲኢኦ አቶ ብርሃን ተድላ የቅርብ ጠንካራ አመራርና ክትትል፣ በሰራተኞችና ባለሙያዎች ትጋት መኾኑን በመጥቀስ ምስጋና አቅርበዋል።
ሆስፒታሉ ለ 333 ጊዜያዊና ቋሚ ሰራተኞች የሥራ ዕድል የፈጠረ ሲኾን ከእነዚህ መካከል 86 ያህሉ ሰብስፔሻስት ሐኪሞች መኾናቸው ተነግሯል።
ኢትዮ-ኢስታንቡል ጠቅላላ ሆስፒታል በተመሰረተ በአጭር ጊዜ ወደውጭ ሀገር በሚወስዱ የህክምና ጥገኝነትን በመቀየር፣ በሀገር ውስጥ ዘመናዊ ህክምና መስጠት የሚያስችል አገልግሎት መዘርጋቱን አስታወቀ።
ኢትዮ-ኢስታንቡል አጠቃላይ ሆስፒታል ሐምሌ 28 ቀን 2018 ዓ.ም ለመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች በሰጠው መግለጫ ላይ እንደተገለጸው ሆስፒታሉ በመሥራቹና ባለራዕዩ ሲኢኦ አቶ ብርሃን ተድላ እየተመራ ከተመሰረተበት ጊዜ ጀምሮ ለታካሚዎች ጥራቱን የጠበቀ የሕክምና አገልግሎት ሲሰጥ የቆየ ሲሆን፣ በተለይም በያዝነው 2018 ዓ.ም ብቻ ከ79 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የተመላላሽ ህክምና አገልግሎት በመስጠትና ከ4 ሺ 500 በላይ የቀዶ ህክምናዎችን በማካሄድ አመርቂ ውጤት አስመዝግቧል።
ሆስፒታሉ እነዚህን ሀገር በቀል አቅሞች በመገንባቱ ቀደም ሲል ለህክምና ወደ ውጭ ሀገር ይሄዱ የነበሩ ታካሚዎችን ቁጥር በመቀነስ የውጭ ምንዛሬን ከማስቀረት ባሻገር የታካሚዎችን ችግር መቅረፍ ችሏል።
በመግለጫው ወቅት የሆስፒታሉ ሜዲካል ዳይሬክተር፣ የአጠቃላይ እና ደረት አካባቢ ቀዶ ህክምና ስፔሻሊስት ተባባሪ ኘሮፌሰር ስዩም ካሣ መርኔ እንደገለጹት፣ ተቋሙ በኢንተርቬንሽናል ካርዲዮሎጂ መስክ ያለ ኦፕሬሽን በደም ስሮች በኩል በሚደረግ ህክምና ጨምሮ በአዋቂና በልጆች የልብ ሕክምና በአጠቃላይ ከ735 በላይ ታካሚዎችን መታደግ ችሏል። አክለውም ይህ አገልግሎት ዓመቱን ሙሉ ሌሊትና ቀን ሳይቋረጥ የሚሰጥ በመሆኑ፣ ከውጭ ሀገር በሚመጡ ጊዜያዊ ዘመቻዎች ላይ ብቻ ጥገኛ የነበረውን አሰራር መቀየር መቻሉን ገልጸዋል።
ሆስፒታሉ በኢትዮጵያውያን ባለሙያዎች በመታገዝ ወደውጪ ሀገር የሚያስኬዱ በተለይ የልብ ሕክምናዎችን 90 በመቶ በሆስፒታሉ መስጠት መቻሉን ጠቅሰዋል።
እንደ ዶክተር ስዩም ገለጻ፣ ሆስፒታሉ በኒውሮሰርጀሪ፣ በኦፕን ካርዲያክ፣ በአጥንትና ስፓይን፣ በኩላሊት፣ በሳምባ፣ የአንጎል፣ የዳሌና የጉልበት ቅየራ እንዲሁም በሚኒማሊ ኢንቬሲቭ (ላፓሮስኮፒክና ቶራኮስኮፒክ) እና ከ46 በላይ ሰብስፔሻሊቲ ህክምና ዘርፎች የላቀ አገልግሎት እየሰጠ ሲሆን፣ የሬዲዮሎጂ ክፍሉም የሰው ሰራሽ አስተውሎት ቴክኖሎጂን በመጠቀም የህክምና ምርመራ ጥራቱን በማሳደግ ላይ ይገኛል ብለዋል።
የሆስፒታሉ የውስጥ ደዌና የአዋቂዎች ኢንተርቬንሽናል የልብ ህክምና ስፔሻሊስት ዶክተር ከፈለኝ ደጀኔ በበኩላቸው እንደገለጹት፣ ከተሰሩት 321 የሕፃናት የልብ ህክምናዎች መከናወናቸውን ጠቁመው 90 የሚጠጋ ድንገተኛ የልብ ደምስር መዘጋት አደጋ ያጋጠማቸውና ታካሚዎች በ24 ሰዓት ድንገተኛ አደጋዎች አገልግሎት ህይወታቸው መታደግ ተችላል ብለዋል። ከእነዚህም ውስጥ ቁጥራቸው ከ90 በላይ የሚኾኑ የውጭ ሀገር ዜጎችና ዲፕሎማቶች እንዲሁም ነፍሰጡር እናቶች ይገኙበታል።
የሆስፒታሉ የቺፍ ኦፕሬሽንስ ዳይሬክተር፣ የአንገትና ጭንቅላት ሰብ-ስፔሻሊስት ዶክተር መለስ ገበየሁ እንደገለጹት ደግሞ፣ ተቋሙ ከንግድ ዓላማው ጎን ለጎን ማህበራዊ ኃላፊነቱን በመወጣት ረገድ ትልቅ ስራ እየሰራ ይገኛል። በሆስፒታሉ ባለቤትና ዋና ስራአስፈጻሚ አቶ ብርሃን ተድላ አማካይነት በተቋቋመው "Heart to Heart Children's Aid" የተሰኘ ፋውንዴሽን በኩል ትልቅ ሥራዎች መከናወናቸውን አስታውሰዋል።
ሜዲካል ዳይሬክተሩ በመጨረሻም ኢትዮ ኢስታንቡል ጠቅላላ ሆስፒታል በሰኔ ወር 2015 ዓ.ም ጀምሮ ወደሥራ መግባቱና በአጭር ጊዜ ውስጥ ከፍተኛ ውጤት መድረስ የቻለው በተቋሙ መስራችና ሲኢኦ አቶ ብርሃን ተድላ የቅርብ ጠንካራ አመራርና ክትትል፣ በሰራተኞችና ባለሙያዎች ትጋት መኾኑን በመጥቀስ ምስጋና አቅርበዋል።
ሆስፒታሉ ለ 333 ጊዜያዊና ቋሚ ሰራተኞች የሥራ ዕድል የፈጠረ ሲኾን ከእነዚህ መካከል 86 ያህሉ ሰብስፔሻስት ሐኪሞች መኾናቸው ተነግሯል።
2 days ago
ቀብር
#ethiopia | የብሔራዊ ሎተሪ አስተዳደር ዋና ሥራ አስኪያጅነትና በተለያዩ መስሪያ ቤቶች ከ40 ዓመታት በላይ በኃላፊነት ሲሠሩ የነበሩት ወይዘሮ መዓዛ ቅጣው አረፉ።
ወይዘሮ መዓዛ ቅጣው በ83 ዓመታቸው ያረፉት ሐምሌ 27 ቀን 2018 ዓ.ም. በአጋጠማቸው ድንገተኛ ሕመም ነው።
ወይዘሮ መዓዛ ቅጣው ሴቶች ከዩኒቨርሲቲ ለመመረቅና በከፍተኛ ኃላፊነት ተመድበው ለመሥራት ብርቅ በነበረበት ጊዜ በውጤት ያለፉ፣ በፋና ወጊነት በሚቆጠር አርአያነት፣ በከፍተኛ ተሳትፎ ሀገራቸውን ሲያገለግሉ ቆይተዋል።
በ1950ዎቹ መጨረሻ ከቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ በኢኮኖሚክስ የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን፣ ከዋሺንግተን ዲሲ አሜሪካን ዩኒቨርሲቲ ሁለተኛ ዲግሪያቸውን በማግኘት ለወጣት ሴቶች ምሳሌ ለመሆን የበቁ ነበሩ።
ወይዘሮ መዓዛ ቅጣው ከ40 ዓመታት በላይ በኃላፊነትና በሥራ መሪነት ባገለገሉባቸው የግልና የመንግሥት መስሪያ ቤቶች አዳዲስ የሥራ ዘዴዎችን በመቀየስና የተቀናጀ አሠራር በማስለመድ ስማቸው በመልካም ሲጠራ ቆይቷል።
በተለይም ለ19 ዓመታት በዋና ሥራ አስኪያጅነት የመሩትን የብሔራዊ ሎተሪ አስተዳደር ትርፋማ ለማድረግ፣ አሠራሩን ለማዘመንና ጠንካራ ተቋም እንዲሆን ያበረከቱት አስተዋጽኦ በጊዜው በነበሩትና ሰነድ በሚመረምሩት ዘንድ የታወቀ ነው።
እንደ ፈጣን ሎተሪ ዓይነቶቹ ከጊዜው ጋር የተጣጣሙ አሠራሮች በብሔራዊ ሎተሪ አስተዳደር እንዲለመዱና የተጠናከሩ እንዲሆኑ ያደረጉት ወይዘሮ መዓዛ ቅጣው ናቸው።
በኢትዮጵያ መድን ድርጅት፣ በኅብረት ኢንሹራንስ፣ በናይል ኢንሹራንስ፣ በብርሃን ኢንሹራንስ በመመሪያ ሥራ አስኪያጅነት እየተመደቡ ተቋሞቹ እንዲጠናከሩ ሙሉ ልምዳቸውንና ችሎታቸውን ማስተላለፋቸውን አብረዋቸው የሠሩት እየመሰከሩላቸው ነው።
ወይዘሮ መዓዛ ቅጣው ትኩረትና ጥንቃቄ ከሚጠይቀው የሥራ መደባቸው ጋር ደርበው እንደ ቤተሰብ መመሪያ ማኅበር ከአንዴም ሁለቴ፣ እንደ ቀይ መስቀል ማኅበር፣ እንደ ኢየሩሳሌም የሕፃናት ማሳደጊያ ድርጅትና በመሣሰሉት ተቋማት ለረጅም ዓመታት በቦርድ ሊቀ መንበርነትና አባልነት፣ በሥራ አስፈጻሚነትም ጭምር ሲሠሩ ቆይተዋል።
ዘለግ ላለውና ውጤታማ ለሆነ ሥራቸው የተለያዩ ሽልማቶችን አግኝተዋል።
እስከ ሕልፈታቸው ድረስ ከሥራ ሳይለዩ በጥናትና በምርምር ሥር ቆይተዋል።
የሁለት ልጆች የሆኑት ወይዘሮ መዓዛ ቅጣው የቀብር ሥነ ሥርዓት ኮተቤ በሚገኘው በመካነ ቅዱሳን ሐና ወኢያቄም ቤተ ክርስቲያን ሐሙስ ሐምሌ 30 ቀን 2018 ዓ.ም. ከቀኑ በ6:00 ሰዓት እንደሚፈጸም ቤተሰቦቻቸው ነግረውናል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#ethiopia | የብሔራዊ ሎተሪ አስተዳደር ዋና ሥራ አስኪያጅነትና በተለያዩ መስሪያ ቤቶች ከ40 ዓመታት በላይ በኃላፊነት ሲሠሩ የነበሩት ወይዘሮ መዓዛ ቅጣው አረፉ።
ወይዘሮ መዓዛ ቅጣው በ83 ዓመታቸው ያረፉት ሐምሌ 27 ቀን 2018 ዓ.ም. በአጋጠማቸው ድንገተኛ ሕመም ነው።
ወይዘሮ መዓዛ ቅጣው ሴቶች ከዩኒቨርሲቲ ለመመረቅና በከፍተኛ ኃላፊነት ተመድበው ለመሥራት ብርቅ በነበረበት ጊዜ በውጤት ያለፉ፣ በፋና ወጊነት በሚቆጠር አርአያነት፣ በከፍተኛ ተሳትፎ ሀገራቸውን ሲያገለግሉ ቆይተዋል።
በ1950ዎቹ መጨረሻ ከቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ በኢኮኖሚክስ የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን፣ ከዋሺንግተን ዲሲ አሜሪካን ዩኒቨርሲቲ ሁለተኛ ዲግሪያቸውን በማግኘት ለወጣት ሴቶች ምሳሌ ለመሆን የበቁ ነበሩ።
ወይዘሮ መዓዛ ቅጣው ከ40 ዓመታት በላይ በኃላፊነትና በሥራ መሪነት ባገለገሉባቸው የግልና የመንግሥት መስሪያ ቤቶች አዳዲስ የሥራ ዘዴዎችን በመቀየስና የተቀናጀ አሠራር በማስለመድ ስማቸው በመልካም ሲጠራ ቆይቷል።
በተለይም ለ19 ዓመታት በዋና ሥራ አስኪያጅነት የመሩትን የብሔራዊ ሎተሪ አስተዳደር ትርፋማ ለማድረግ፣ አሠራሩን ለማዘመንና ጠንካራ ተቋም እንዲሆን ያበረከቱት አስተዋጽኦ በጊዜው በነበሩትና ሰነድ በሚመረምሩት ዘንድ የታወቀ ነው።
እንደ ፈጣን ሎተሪ ዓይነቶቹ ከጊዜው ጋር የተጣጣሙ አሠራሮች በብሔራዊ ሎተሪ አስተዳደር እንዲለመዱና የተጠናከሩ እንዲሆኑ ያደረጉት ወይዘሮ መዓዛ ቅጣው ናቸው።
በኢትዮጵያ መድን ድርጅት፣ በኅብረት ኢንሹራንስ፣ በናይል ኢንሹራንስ፣ በብርሃን ኢንሹራንስ በመመሪያ ሥራ አስኪያጅነት እየተመደቡ ተቋሞቹ እንዲጠናከሩ ሙሉ ልምዳቸውንና ችሎታቸውን ማስተላለፋቸውን አብረዋቸው የሠሩት እየመሰከሩላቸው ነው።
ወይዘሮ መዓዛ ቅጣው ትኩረትና ጥንቃቄ ከሚጠይቀው የሥራ መደባቸው ጋር ደርበው እንደ ቤተሰብ መመሪያ ማኅበር ከአንዴም ሁለቴ፣ እንደ ቀይ መስቀል ማኅበር፣ እንደ ኢየሩሳሌም የሕፃናት ማሳደጊያ ድርጅትና በመሣሰሉት ተቋማት ለረጅም ዓመታት በቦርድ ሊቀ መንበርነትና አባልነት፣ በሥራ አስፈጻሚነትም ጭምር ሲሠሩ ቆይተዋል።
ዘለግ ላለውና ውጤታማ ለሆነ ሥራቸው የተለያዩ ሽልማቶችን አግኝተዋል።
እስከ ሕልፈታቸው ድረስ ከሥራ ሳይለዩ በጥናትና በምርምር ሥር ቆይተዋል።
የሁለት ልጆች የሆኑት ወይዘሮ መዓዛ ቅጣው የቀብር ሥነ ሥርዓት ኮተቤ በሚገኘው በመካነ ቅዱሳን ሐና ወኢያቄም ቤተ ክርስቲያን ሐሙስ ሐምሌ 30 ቀን 2018 ዓ.ም. ከቀኑ በ6:00 ሰዓት እንደሚፈጸም ቤተሰቦቻቸው ነግረውናል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
2 days ago
ይህን እሽግ እንደተራ መክሰስ ለገበያ ማቅረብ ወንጀል ነው!
#ethiopia | በከባድ የምግብ እጥረት የተጎዱ ሕፃናትን ሕይወት ለማዳን የሚሰጠው አጣዳፊ የምግብ መድኃኒት (RUTF) ወይ በተለምዶ ስሙ ፕላምፕሌት በገበያ ላይ ለንግድ መቅረቡና ለክብደት መጨመሪያ መዋሉ ከፍተኛ የሞራልና የሕግ ተጠያቂነትን የሚያስከትል ወንጀል መሆኑ ተገለጸ።
በሞት አፋፍ ላይ የሚገኙ ሕፃናትን ለማዳን በልዩ ሁኔታ የተዘጋጀውን ይህን ሕይወት አድን እሽግ እንደ ተራ መክሰስ ለገበያ ማቅረብ በእርግጥም ህክምናው ለሚገባቸው ሕፃናት የሚደርሰውን እርዳታ በመንጠቅ ሕይወታቸውን ለሞት አደጋ የሚያጋልጥ ተግባር ነው።
በሌላ በኩል ይህ ምርት በካሎሪ፣ በቅባትና በቫይታሚኖች እጅግ የበለፀገ በመሆኑ ጤናማ ሰዎች ሳያስፈልጋቸው ሲመገቡት ለከፍተኛ የኩላሊትና የጉበት ጫና፣ ለደም ስኳርና ቅባት መዛባት እንዲሁም ለቫይታሚን መርዝነት ያጋልጣቸዋል።
በመሆኑም በነፃ ወይም በሕክምና ተቋማት በኩል ለተቸገሩ ሕፃናት የተላከን እርዳታ መሸጥም ሆነ መግዛት በሕግ የሚያስጠይቅ ወንጀል በመሆኑ፣ ሕይወት አድን መድኃኒቶች የንግድ ዕቃ አለመሆናቸውን ተረድቶ ኅብረተሰቡ ከዚህ ድርጊት ሊቆጠብ እንደሚገባ መልእክት ተላልፏል።
(via ጤና)
በያፌት ገ/ህይወት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#ethiopia | በከባድ የምግብ እጥረት የተጎዱ ሕፃናትን ሕይወት ለማዳን የሚሰጠው አጣዳፊ የምግብ መድኃኒት (RUTF) ወይ በተለምዶ ስሙ ፕላምፕሌት በገበያ ላይ ለንግድ መቅረቡና ለክብደት መጨመሪያ መዋሉ ከፍተኛ የሞራልና የሕግ ተጠያቂነትን የሚያስከትል ወንጀል መሆኑ ተገለጸ።
በሞት አፋፍ ላይ የሚገኙ ሕፃናትን ለማዳን በልዩ ሁኔታ የተዘጋጀውን ይህን ሕይወት አድን እሽግ እንደ ተራ መክሰስ ለገበያ ማቅረብ በእርግጥም ህክምናው ለሚገባቸው ሕፃናት የሚደርሰውን እርዳታ በመንጠቅ ሕይወታቸውን ለሞት አደጋ የሚያጋልጥ ተግባር ነው።
በሌላ በኩል ይህ ምርት በካሎሪ፣ በቅባትና በቫይታሚኖች እጅግ የበለፀገ በመሆኑ ጤናማ ሰዎች ሳያስፈልጋቸው ሲመገቡት ለከፍተኛ የኩላሊትና የጉበት ጫና፣ ለደም ስኳርና ቅባት መዛባት እንዲሁም ለቫይታሚን መርዝነት ያጋልጣቸዋል።
በመሆኑም በነፃ ወይም በሕክምና ተቋማት በኩል ለተቸገሩ ሕፃናት የተላከን እርዳታ መሸጥም ሆነ መግዛት በሕግ የሚያስጠይቅ ወንጀል በመሆኑ፣ ሕይወት አድን መድኃኒቶች የንግድ ዕቃ አለመሆናቸውን ተረድቶ ኅብረተሰቡ ከዚህ ድርጊት ሊቆጠብ እንደሚገባ መልእክት ተላልፏል።
(via ጤና)
በያፌት ገ/ህይወት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
3 days ago
805.3 ሚሊዮን ችግኞች በአንድ ጀምበር፤ የኢትዮጵያውያን ተአምራዊ ውሎ
*********************
ዛሬ በመላው ኢትዮጵያ “ተስፋን እንትከል” በሚል መሪ ቃል በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎች በአንድ ልብ እና በአንድ መንፈስ በመንቀሳቀስ በአንድ ጀምበር 805.3 ሚሊዮን ችግኞችን በመትከል አዲስ ታሪክ ፅፈዋል።
ኢትዮጵያውያን የዕድሜ ልዩነት ሳይበግራቸው ከሕፃናት እስከ አዛውንት ከአካል ጉዳተኞች እስከ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ሃላፊዎች በጋራ በመሆን አረንጓዴ አሻራቸውን አሳርፈዋል። ይህ የነቃ ተሳትፎም የማህበረሰቡን አንድነትና ለአካባቢ ጥበቃ ያላቸውን ጽኑ ቁርጠኝነት በግልጽ ያሳየ ነው።
ይህ መርሃ ግብር ልጆችን በማሳተፍ ስለ አካባቢ ጥበቃ አስፈላጊነት በተግባር የሚማሩበት ልዩ መድረክ ሆኗል። ህፃናት ከወዲሁ የችግኝ እንክብካቤን እንደ ባህል እንዲለምዱና የነገዋን አረንጓዴ አገር የመረከብ ሃላፊነታቸውን ገና በሕፃንነታቸው እንዲረዱ ያግዛል።
በተጨማሪም ሀገራዊ አንድነትን በተግባር ከመግለጹ በላይ ለአየር ንብረት ለውጥ አሳሳቢ ፈተናዎች ምላሽ ለመስጠትና የኢትዮጵያን የመጻኢ ዘመን ዕጣ ፈንታ በጽኑ መሠረት ላይ ለመገንባት ያለመ ንቅናቄ ነው።
ይህ የተቀናጀ ሀገራዊ ርብርብ የትናንቱ የአድዋ ድል የነፃነት አርበኝነት በተፈጥሮ ጥበቃ የሚደገምበት የዘመናችን የጀግንነት ምዕራፍ ተደርጎ ይወሰዳል።
ቀደምት አባቶች በአድዋ ተራሮች ላይ ልዩነቶቻቸውን አክስመው ለሀገር ነፃነት እንደቆሙ ሁሉ የዛሬው ትውልድም ድህነትንና የተፈጥሮ መራቆትን ለማሸነፍ ዕውቀቱን ጉልበቱንና ፍቅሩን አስተባብሮ ኢትዮጵያን አረንጓዴ የማልበስ ኃላፊነቱን እየተወጣ ይገኛል።
የምትተከለው እያንዳንዷ ችግኝ የተራቆቱ መሬቶች መልሰው እንዲያገግሙ የአፈር መሸርሸርና የጎርፍ አደጋዎች እንዲቀንሱ እንዲሁም የከርሰ ምድር ውሃ እንዲበለጽግ በማድረግ ረገድ ትልቁን ድርሻ ታበረክታለች።
ከአካባቢ ጥበቃ ፋይዳው ባሻገር መርሐ ግብሩ የሀገሪቱን ምጣኔ ሀብት የሚያነቃቃ ታላቅ ዕድል ፈጥሯል። በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ወጣቶች በችግኝ ማፍላት በጉድጓድ ዝግጅትና በተከላ ሥራዎች በመሰማራት ሰፊ የሥራ ዕድል ያገኙ ሲሆን በተለይም እንደ ቡና፣ አቮካዶና ማንጎ ያሉ የኢኮኖሚ ጠቀሜታ ያላቸው ተክሎች ትኩረት ማግኘታቸው ለአርሶ አደሩ ተጨማሪ የገቢ ምንጭ በመሆን የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ መሠረት ጥሏል።
በተጨማሪም ይህ ሀገራዊ ጥረት በዓለም አቀፍ ደረጃ የአየር ንብረት መዛባትን ለመቋቋም የሚረዳና ኢትዮጵያ ለዓለም አረንጓዴ ልማት ያላትን ቁርጠኝነት የሚያሳይ ሕያው ውርስ ነው።
ይህ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በቅድመ ዝግጅት ከተያዘው እቅድ በላይ በመፈጸም በዛሬዉ ዕለት ብቻ 805.3 ሚሊዮን ችግኞች የተተከሉ ሲሆን 26.2 ሚሊየን ሰዎች ተሳትፈዋል በዚህም 291.4 ሺህ ሄክታር መሬት መሸፈን ተችሏል በዚህም ታሪካዊ ስኬት ተመዝግቧል።
ይህ በዓይነቱ ልዩ የሆነው አገራዊ የችግኝ ተከላ ዘመቻ የህዝባችንን የተቀናጀ የተቀናጀ ጥረት እና ለአካባቢ ጥበቃ ያለውን ቁርጠኝነት በአለም አቀፍ ደረጃ ታላቅ ሁነት ሆኖ አልፏል።
በዘንድሮው አመት እስካሁን ባለው ጊዜ ከ6.5 ቢሊዮን በላይ ችግኞች መተከላቸው የተገለጸ ሲሆን የተያዘውን አጠቃላይ እቅድ ለማጠናቀቅ ቀሪ የሆኑት 1.5 ቢሊዮን ችግኞች ደግሞ በሚቀጥሉት ወራት ተተክለው የሚጠናቀቁ ይሆናል።
የዚህ ታሪካዊ ዘመቻ እውነተኛ ስኬት የሚለካው በተከላው ሂደት ብቻ ሳይሆን ከተከላ በኋላ በሚደረግ ቀጣይነት ያለው እንክብካቤና ጥበቃ በመሆኑ እያንዳንዱ ዜጋ የተከላቸውን ችግኞች ተንከባክቦ ለፍሬ የማብቃት አደራ አለበት።
በብሌን ደምበሎ
*********************
ዛሬ በመላው ኢትዮጵያ “ተስፋን እንትከል” በሚል መሪ ቃል በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎች በአንድ ልብ እና በአንድ መንፈስ በመንቀሳቀስ በአንድ ጀምበር 805.3 ሚሊዮን ችግኞችን በመትከል አዲስ ታሪክ ፅፈዋል።
ኢትዮጵያውያን የዕድሜ ልዩነት ሳይበግራቸው ከሕፃናት እስከ አዛውንት ከአካል ጉዳተኞች እስከ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ሃላፊዎች በጋራ በመሆን አረንጓዴ አሻራቸውን አሳርፈዋል። ይህ የነቃ ተሳትፎም የማህበረሰቡን አንድነትና ለአካባቢ ጥበቃ ያላቸውን ጽኑ ቁርጠኝነት በግልጽ ያሳየ ነው።
ይህ መርሃ ግብር ልጆችን በማሳተፍ ስለ አካባቢ ጥበቃ አስፈላጊነት በተግባር የሚማሩበት ልዩ መድረክ ሆኗል። ህፃናት ከወዲሁ የችግኝ እንክብካቤን እንደ ባህል እንዲለምዱና የነገዋን አረንጓዴ አገር የመረከብ ሃላፊነታቸውን ገና በሕፃንነታቸው እንዲረዱ ያግዛል።
በተጨማሪም ሀገራዊ አንድነትን በተግባር ከመግለጹ በላይ ለአየር ንብረት ለውጥ አሳሳቢ ፈተናዎች ምላሽ ለመስጠትና የኢትዮጵያን የመጻኢ ዘመን ዕጣ ፈንታ በጽኑ መሠረት ላይ ለመገንባት ያለመ ንቅናቄ ነው።
ይህ የተቀናጀ ሀገራዊ ርብርብ የትናንቱ የአድዋ ድል የነፃነት አርበኝነት በተፈጥሮ ጥበቃ የሚደገምበት የዘመናችን የጀግንነት ምዕራፍ ተደርጎ ይወሰዳል።
ቀደምት አባቶች በአድዋ ተራሮች ላይ ልዩነቶቻቸውን አክስመው ለሀገር ነፃነት እንደቆሙ ሁሉ የዛሬው ትውልድም ድህነትንና የተፈጥሮ መራቆትን ለማሸነፍ ዕውቀቱን ጉልበቱንና ፍቅሩን አስተባብሮ ኢትዮጵያን አረንጓዴ የማልበስ ኃላፊነቱን እየተወጣ ይገኛል።
የምትተከለው እያንዳንዷ ችግኝ የተራቆቱ መሬቶች መልሰው እንዲያገግሙ የአፈር መሸርሸርና የጎርፍ አደጋዎች እንዲቀንሱ እንዲሁም የከርሰ ምድር ውሃ እንዲበለጽግ በማድረግ ረገድ ትልቁን ድርሻ ታበረክታለች።
ከአካባቢ ጥበቃ ፋይዳው ባሻገር መርሐ ግብሩ የሀገሪቱን ምጣኔ ሀብት የሚያነቃቃ ታላቅ ዕድል ፈጥሯል። በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ወጣቶች በችግኝ ማፍላት በጉድጓድ ዝግጅትና በተከላ ሥራዎች በመሰማራት ሰፊ የሥራ ዕድል ያገኙ ሲሆን በተለይም እንደ ቡና፣ አቮካዶና ማንጎ ያሉ የኢኮኖሚ ጠቀሜታ ያላቸው ተክሎች ትኩረት ማግኘታቸው ለአርሶ አደሩ ተጨማሪ የገቢ ምንጭ በመሆን የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ መሠረት ጥሏል።
በተጨማሪም ይህ ሀገራዊ ጥረት በዓለም አቀፍ ደረጃ የአየር ንብረት መዛባትን ለመቋቋም የሚረዳና ኢትዮጵያ ለዓለም አረንጓዴ ልማት ያላትን ቁርጠኝነት የሚያሳይ ሕያው ውርስ ነው።
ይህ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በቅድመ ዝግጅት ከተያዘው እቅድ በላይ በመፈጸም በዛሬዉ ዕለት ብቻ 805.3 ሚሊዮን ችግኞች የተተከሉ ሲሆን 26.2 ሚሊየን ሰዎች ተሳትፈዋል በዚህም 291.4 ሺህ ሄክታር መሬት መሸፈን ተችሏል በዚህም ታሪካዊ ስኬት ተመዝግቧል።
ይህ በዓይነቱ ልዩ የሆነው አገራዊ የችግኝ ተከላ ዘመቻ የህዝባችንን የተቀናጀ የተቀናጀ ጥረት እና ለአካባቢ ጥበቃ ያለውን ቁርጠኝነት በአለም አቀፍ ደረጃ ታላቅ ሁነት ሆኖ አልፏል።
በዘንድሮው አመት እስካሁን ባለው ጊዜ ከ6.5 ቢሊዮን በላይ ችግኞች መተከላቸው የተገለጸ ሲሆን የተያዘውን አጠቃላይ እቅድ ለማጠናቀቅ ቀሪ የሆኑት 1.5 ቢሊዮን ችግኞች ደግሞ በሚቀጥሉት ወራት ተተክለው የሚጠናቀቁ ይሆናል።
የዚህ ታሪካዊ ዘመቻ እውነተኛ ስኬት የሚለካው በተከላው ሂደት ብቻ ሳይሆን ከተከላ በኋላ በሚደረግ ቀጣይነት ያለው እንክብካቤና ጥበቃ በመሆኑ እያንዳንዱ ዜጋ የተከላቸውን ችግኞች ተንከባክቦ ለፍሬ የማብቃት አደራ አለበት።
በብሌን ደምበሎ
4 days ago
በኦቶና ሆስፒታል የላብራቶሪ መሳሪያዎችን ሊሰርቅ የነበረ የጥበቃ ሰራተኛ እጅ ከፍንጂ ተያዘ
በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ኮምፕሬሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል (ኦቶና) ሦስት ወሳኝ የላብራቶሪ ማይክሮስኮፖችን አውጥቶ ለመሰወር ሲሞክር የነበረ የጥበቃ ሰራተኛ በተረኛ ጥበቃዎች ብርቱ ክትትልና ተጋድሎ እጅ ከፍንጂ መያዙ ተገለጸ።
በትላትናው እለተ የተፈጸመው ይህ ድርጊት ተራ የሕክምና ዕቃ ስርቆት ሳይሆን፣ የሺዎችን ሕይወት እና የሆስፒታሉን ዕለታዊ የሕክምና አገልግሎት ቀጥተኛ አደጋ ላይ የጣለ ከባድ ወንጀል መሆኑን ባለሙያዎች ይናገራሉ።
ተጠርጣሪው ግለሰብ የሕክምና መገልገያዎቹን ደብቆ ከሆስፒታሉ ግቢ ሊያወጣ ሲል በተረኛ ባልደረቦቹ ንቁ ክትትል በቁጥጥር ስር ውሏል። ድርጊቱ በግለሰቡ ብቻ የተፈጸመ ሳይሆን በጀርባ ያሉ አመቻቾችና አቀናባሪዎች እንዳሉበት በመጠረጠሩ፣ ወንጀሉን ያስተባበሩ አካላት በሙሉ ተለይተው ተገቢው የሕግ ትርጉም እንዲሰጣቸውና አስተማሪ ቅጣት እንዲያገኙ ጉዳዩ በትኩረት እየተከታተለ ይገኛል።
በአንድ አጠቃላይ ሆስፒታል ውስጥ ማይክሮስኮፕ ማለት የተደበቁ በሽታዎችን አውጥቶ በማሳየት የሕሙማንን ሕይወት የሚያስጥል ዋና መመርመሪያ መሳሪያ ነው።
እነዚህን መገልገያዎች ማጣት በሕሙማን ላይ የሚከተሉትን ከባድ የጤና አደጋዎች ያስከትላል፦
እንደ ወባ፣ ቲቢ እና የተለያዩ ከባድ የባክቴሪያ ኢንፌክሽኖችን በፍጥነት በመመርመር አስቸኳይ የሕክምና ውሳኔ ለመስጠት ያገለግላሉ።
የደም ማነስን (Anemia) እና የደም ካንሰርን (Leukemia) በጥንቃቄ ለይቶ ለማወቅ ወሳኝ መገልገያዎች ናቸው።
እነዚህ መሳሪያዎች ከአገልግሎት ውጭ ሲሆኑ የላብራቶሪ ውጤቶች ይዘገያሉ፤ ይህም በተለይ በፅኑ ሕሙማን፣ በሕፃናትና ነፍሰ ጡራት ሕይወት ላይ የቀጥታ አደጋ ይደቅናል።
የሕዝብና የመንግሥት ሀብት የሆኑትን የሕክምና መገልገያዎች ከስርቆትና ከእጅ አዙር ሴራ መጠበቅ የሁላችንም ኃላፊነት ነው።
በሆስፒታሉ ግቢ ውስጥ የታየው የተረኛ ጥበቃዎች ንቅናቄ የሚደነቅ ሲሆን፣ የወንጀሉ ተሳታፊዎች በሙሉ ለሕግ እንዲቀርቡ የጀመረው ክትትል ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል።
Via ጉርሻ page
በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ኮምፕሬሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል (ኦቶና) ሦስት ወሳኝ የላብራቶሪ ማይክሮስኮፖችን አውጥቶ ለመሰወር ሲሞክር የነበረ የጥበቃ ሰራተኛ በተረኛ ጥበቃዎች ብርቱ ክትትልና ተጋድሎ እጅ ከፍንጂ መያዙ ተገለጸ።
በትላትናው እለተ የተፈጸመው ይህ ድርጊት ተራ የሕክምና ዕቃ ስርቆት ሳይሆን፣ የሺዎችን ሕይወት እና የሆስፒታሉን ዕለታዊ የሕክምና አገልግሎት ቀጥተኛ አደጋ ላይ የጣለ ከባድ ወንጀል መሆኑን ባለሙያዎች ይናገራሉ።
ተጠርጣሪው ግለሰብ የሕክምና መገልገያዎቹን ደብቆ ከሆስፒታሉ ግቢ ሊያወጣ ሲል በተረኛ ባልደረቦቹ ንቁ ክትትል በቁጥጥር ስር ውሏል። ድርጊቱ በግለሰቡ ብቻ የተፈጸመ ሳይሆን በጀርባ ያሉ አመቻቾችና አቀናባሪዎች እንዳሉበት በመጠረጠሩ፣ ወንጀሉን ያስተባበሩ አካላት በሙሉ ተለይተው ተገቢው የሕግ ትርጉም እንዲሰጣቸውና አስተማሪ ቅጣት እንዲያገኙ ጉዳዩ በትኩረት እየተከታተለ ይገኛል።
በአንድ አጠቃላይ ሆስፒታል ውስጥ ማይክሮስኮፕ ማለት የተደበቁ በሽታዎችን አውጥቶ በማሳየት የሕሙማንን ሕይወት የሚያስጥል ዋና መመርመሪያ መሳሪያ ነው።
እነዚህን መገልገያዎች ማጣት በሕሙማን ላይ የሚከተሉትን ከባድ የጤና አደጋዎች ያስከትላል፦
እንደ ወባ፣ ቲቢ እና የተለያዩ ከባድ የባክቴሪያ ኢንፌክሽኖችን በፍጥነት በመመርመር አስቸኳይ የሕክምና ውሳኔ ለመስጠት ያገለግላሉ።
የደም ማነስን (Anemia) እና የደም ካንሰርን (Leukemia) በጥንቃቄ ለይቶ ለማወቅ ወሳኝ መገልገያዎች ናቸው።
እነዚህ መሳሪያዎች ከአገልግሎት ውጭ ሲሆኑ የላብራቶሪ ውጤቶች ይዘገያሉ፤ ይህም በተለይ በፅኑ ሕሙማን፣ በሕፃናትና ነፍሰ ጡራት ሕይወት ላይ የቀጥታ አደጋ ይደቅናል።
የሕዝብና የመንግሥት ሀብት የሆኑትን የሕክምና መገልገያዎች ከስርቆትና ከእጅ አዙር ሴራ መጠበቅ የሁላችንም ኃላፊነት ነው።
በሆስፒታሉ ግቢ ውስጥ የታየው የተረኛ ጥበቃዎች ንቅናቄ የሚደነቅ ሲሆን፣ የወንጀሉ ተሳታፊዎች በሙሉ ለሕግ እንዲቀርቡ የጀመረው ክትትል ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል።
Via ጉርሻ page
5 days ago
አሜን! ቅድስት ኪዳነ ምሕረት እናታችን በምልጃዋ አለው ልጆቼ ትበለን ! 🙏
"አሜን"
ብሎ የሚጽፍ ሁሉ፣ በእግዚአብሔር ፈቃድ የልቡን መልካም ምኞት ይፈጽምለት፤ በቅድስት ኪዳነ ምሕረት ምልጃ ከመከራ ያድነው፣ ያልታሰበ በረከትና ደስታ ወደ ቤቱ ያስገባለት። አሜን!
በዚህ የጾመ ፍልሰታ ወቅት፣ ሕፃናት ክርስትና እንዲነሱ፣ ምዕመናንም እንዲቆርቡና እንዲያስቀድሱ የሚደረገውን አገልግሎት በአቅማችሁ ደግፉ።
የገጠሪቷን ቤተክርስቲያን
የንግድ ባንክ
1000644937128
(የቤተክርስቲያኑ አካውንት)
📞 ለበለጠ መረጃ: 0954441078
📩 ስመ ክርስትናችሁን በቴሌግራም ላኩልን፤ ዘወትር በጸሎት እናስባችኋለን።
"ጥቂት አድርጋችሁ ብዙ አግኙ!"
"አሜን"
ብሎ የሚጽፍ ሁሉ፣ በእግዚአብሔር ፈቃድ የልቡን መልካም ምኞት ይፈጽምለት፤ በቅድስት ኪዳነ ምሕረት ምልጃ ከመከራ ያድነው፣ ያልታሰበ በረከትና ደስታ ወደ ቤቱ ያስገባለት። አሜን!
በዚህ የጾመ ፍልሰታ ወቅት፣ ሕፃናት ክርስትና እንዲነሱ፣ ምዕመናንም እንዲቆርቡና እንዲያስቀድሱ የሚደረገውን አገልግሎት በአቅማችሁ ደግፉ።
የገጠሪቷን ቤተክርስቲያን
የንግድ ባንክ
1000644937128
(የቤተክርስቲያኑ አካውንት)
📞 ለበለጠ መረጃ: 0954441078
📩 ስመ ክርስትናችሁን በቴሌግራም ላኩልን፤ ዘወትር በጸሎት እናስባችኋለን።
"ጥቂት አድርጋችሁ ብዙ አግኙ!"
Sponsored by
Surafel
7 days ago
በኢትዮጵያ የኪነ-ጥበብ ዘርፍ የሚታዩ የክህሎትና የመዋቅር ችግሮችን ለመቅረፍ አዲስ የጋራ ስምምነት ተደረገ!
#fastmereja :-በኢትዮጵያ የኪነ-ጥበብ ዘርፍ የሚታዩ መዋቅራዊና የክህሎት ችግሮችን ለመቅረፍ የአዲስ አበባ ቴአትር ቤቶች አስተዳደር ድርጅት እና የአባ ለታ አክቲንግ አካዳሚ በጋራ ለመስራት በዛሬዉ እለት ተፈራረሙ።
በአዲሱ አስተዳደራዊ መዋቅር ስር የሚገኙትን ብሔራዊ ቴአትር፣ ሀገርፍቅር ቴአትር፣ የአዲስ አበባ ባህልና ቱሪዝም (ባህል አዳራሽ)፣ ራስ ቴአትር እና የሕፃናትና ወጣቶች ቴአትርን የሚያስተዳድረው ተቋሙ፤ ከግል ዘርፍ አጋሮች ጋር አብሮ ለመሥራት ባቀደው መሠረት ይፋዊ ስምምነቱን አድርጓል።
በስምምነቱ መሠረት የአስተዳደሩን የዘመናት የታሪክና የልምድ ክምችት ከአካዳሚው ዘመናዊና ፈጠራ የታከለበት የአሰልጠና ዘዴ ጋር በማዋሃድ በቴአትር፣ በሙዚቃ፣ በፊልምና ተዛማጅ የኪነ-ጥበብ ዘርፎች ሰፊ ስልጠናዎች በጋራ እንደሚሰጡ ተገልጿል።
በተጨማሪም የኢትዮጵያን ባህል፣ ታሪክና ወግ የሚያንፀባርቁ ጥበባዊ ሁነቶችንና ትላልቅ ፕሮዳክሽኖችን በጋራ በማዘጋጀት ለሕዝብ ለማቅረብ፣ እንዲሁም ከግጥም ምሽቶች እስከ ታላላቅ የኪነ-ጥበብ ፌስቲቫሎች ድረስ ያሉ መድረኮችን ለማስፋፋት መታቀዱም ነዉ የተገለፀዉ።
የአባ ለታ አክቲንግ አካዳሚ ዋና መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ሌንጮ ፍቅሩ በፊርማ ሥነ-ሥርዓቱ ወቅት እንደገለጹት፤ አካዳሚው ከተመሠረተበት ባለፉት ሁለት ዓመታት ውስጥ በርካታ ወጣትና ህጻናት
ተማሪዎችን አብቅቶ ያስመረቀ ሲሆን፣ በተለይም በልጆች አክቲንግ ዘርፍ አበራች አስተዋጽኦ አበርክቷል ሲሉ ተናግረዋል።
አቶ ሌንጮ አክለው እንደገለጹት፣ አካዳሚው እስካሁን በነበረው ጉዞ የቦታ፣ የሎኬሽን እና የትወና ቁሳቁሶች (Props) እጥረት ዋና ዋና ማነቆዎች እንደነበሩበት አስታውሰዋል።
ሆኖም ከአዲስ አበባ ቴአትር ቤቶች አስተዳደር ድርጅት ጋር የተደረገው ይህ ይፋዊ ስምምነት እነዚህን የሎጅስቲክስና የቦታ ችግሮች በዘላቂነት በመቅረፍ፣ የሰለጠኑ አዳዲስ ከዋክብትን ወደ ታሪካዊ የቴአትር መድረኮች ለማውጣት ትልቅ እድል የሚፈጥር መሆኑን ገልጸዋል።
#fastmereja :-በኢትዮጵያ የኪነ-ጥበብ ዘርፍ የሚታዩ መዋቅራዊና የክህሎት ችግሮችን ለመቅረፍ የአዲስ አበባ ቴአትር ቤቶች አስተዳደር ድርጅት እና የአባ ለታ አክቲንግ አካዳሚ በጋራ ለመስራት በዛሬዉ እለት ተፈራረሙ።
በአዲሱ አስተዳደራዊ መዋቅር ስር የሚገኙትን ብሔራዊ ቴአትር፣ ሀገርፍቅር ቴአትር፣ የአዲስ አበባ ባህልና ቱሪዝም (ባህል አዳራሽ)፣ ራስ ቴአትር እና የሕፃናትና ወጣቶች ቴአትርን የሚያስተዳድረው ተቋሙ፤ ከግል ዘርፍ አጋሮች ጋር አብሮ ለመሥራት ባቀደው መሠረት ይፋዊ ስምምነቱን አድርጓል።
በስምምነቱ መሠረት የአስተዳደሩን የዘመናት የታሪክና የልምድ ክምችት ከአካዳሚው ዘመናዊና ፈጠራ የታከለበት የአሰልጠና ዘዴ ጋር በማዋሃድ በቴአትር፣ በሙዚቃ፣ በፊልምና ተዛማጅ የኪነ-ጥበብ ዘርፎች ሰፊ ስልጠናዎች በጋራ እንደሚሰጡ ተገልጿል።
በተጨማሪም የኢትዮጵያን ባህል፣ ታሪክና ወግ የሚያንፀባርቁ ጥበባዊ ሁነቶችንና ትላልቅ ፕሮዳክሽኖችን በጋራ በማዘጋጀት ለሕዝብ ለማቅረብ፣ እንዲሁም ከግጥም ምሽቶች እስከ ታላላቅ የኪነ-ጥበብ ፌስቲቫሎች ድረስ ያሉ መድረኮችን ለማስፋፋት መታቀዱም ነዉ የተገለፀዉ።
የአባ ለታ አክቲንግ አካዳሚ ዋና መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ሌንጮ ፍቅሩ በፊርማ ሥነ-ሥርዓቱ ወቅት እንደገለጹት፤ አካዳሚው ከተመሠረተበት ባለፉት ሁለት ዓመታት ውስጥ በርካታ ወጣትና ህጻናት
ተማሪዎችን አብቅቶ ያስመረቀ ሲሆን፣ በተለይም በልጆች አክቲንግ ዘርፍ አበራች አስተዋጽኦ አበርክቷል ሲሉ ተናግረዋል።
አቶ ሌንጮ አክለው እንደገለጹት፣ አካዳሚው እስካሁን በነበረው ጉዞ የቦታ፣ የሎኬሽን እና የትወና ቁሳቁሶች (Props) እጥረት ዋና ዋና ማነቆዎች እንደነበሩበት አስታውሰዋል።
ሆኖም ከአዲስ አበባ ቴአትር ቤቶች አስተዳደር ድርጅት ጋር የተደረገው ይህ ይፋዊ ስምምነት እነዚህን የሎጅስቲክስና የቦታ ችግሮች በዘላቂነት በመቅረፍ፣ የሰለጠኑ አዳዲስ ከዋክብትን ወደ ታሪካዊ የቴአትር መድረኮች ለማውጣት ትልቅ እድል የሚፈጥር መሆኑን ገልጸዋል።
8 days ago
(ዘ-ሐበሻ ስፖርት) እግር ኳስ አንዳንዴ ከስፖርትነት አልፎ ድንቅ እና ስሜት ቀስቃሽ ታሪኮችን ይጽፋል። የ8 ወር ህጻን እያለ በሀገሩ ሄይቲ በደረሰው እና ከ300 ሺህ በላይ ሰዎችን ህይወት በከፋ ሁኔታ በቀጠፈው አሰቃቂ የመሬት መንቀጥቀጥ ወቅት፣ ከተአምር በተጠጋ ሁኔታ የተረፈው ወጣት፤ ዛሬ በዓለም እግር ኳስ ታላቁን ሰማያዊ እና ነጭ ማሊያ ለብሶ አዲስ ታሪክ ጽፏል።
የ17 ዓመቱ ስቲቨን "ኪኪ" ራሞስ ለአርጀንቲና ከ17 ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድን በመሰለፍ፣ በሄይቲ ተወልዶ የታላቋን ደቡብ አሜሪካ ሀገር ማሊያ የለበሰ የመጀመሪያው ተጫዋች መሆን ችሏል!
በታዋቂው የቬሌዝ ሳርስፊልድ አካዳሚ ውስጥ በክንፍ አጥቂነት የሚያበራው ይህ ታዳጊ፣ አርጀንቲና ኢኳዶርን 2ለ1 ባሸነፈችበት ጨዋታ ላይ ለአልቢሴሌስቴዎች የመጀመሪያ ጨዋታውን አድርጓል። በጨዋታው ላይ ድንቅ እንቅስቃሴ በማሳየት እና ሁለት ግቦችን በማስቆጠር ቡድኑን ለድል ያበቃው ኪኪ ራሞስ፣ በዓለም እግር ኳስ ግዙፍ ስም ባላቸው አርጀንቲናውያን ዘንድ ስሙን በወርቅ ቀለም ጽፏል።
በ2009 በፖርት-ኦ-ፕሪንስ ሄይቲ የተወለደው ኪኪ፣ ለአርጀንቲና በማንኛውም የዕድሜ እርከን ብሔራዊ ቡድን ውስጥ የተሰለፈ የመጀመሪያው በሄይቲ የተወለደ ጥቁር ተጫዋች በመሆን አዲስ የኢንተርናሽናል እግር ኳስ ምዕራፍ ከፍቷል።
የኪኪ የህይወት ታሪክ ልክ እንደ አስደናቂ የፊልም ስክሪፕት ነው። እ.ኤ.አ በ2010 በሄይቲ ደርሶ በነበረው አውዳሚ የመሬት መንቀጥቀጥ ወቅት ገና የ8 ወር ህጻን የነበረው ኪኪ፣ በነበረበት የሕፃናት ማደሪያ ጣቢያ ውስጥ ጉዳት ሳይደርስበት ከተረፉት በጣም ጥቂት ህጻናት አንዱ ነበር።
ባዮሎጂካል ወላጆቹ አርጀንቲናውያን ባይሆኑም፣ አንድ ደግ ልብ ያላቸው አርጀንቲናውያን ባልና ሚስት በጉዲፈቻ ወስደው ወደ ቦነስ አይረስ አመጡት። ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ህይወቱን ሙሉ በአርጀንቲና ያሳለፈው፣ ቋንቋውን እና ባህሉን ለምዶ ያደገው ኪኪ፣ የሀገሪቱን ዜግነት በመያዝ ለብሔራዊ ቡድኑ የመጫወት ህጋዊ መብትን አግኝቷል።
የኪኪ ራሞስ ታሪክ ይፋ መሆንን ተከትሎ በአርጀንቲናውያን የእግር ኳስ አፍቃሪዎች ዘንድ ከፍተኛ ደስታ እና ኩራት ተፈጥሯል። በጨዋታው ካሳየው ከፍተኛ ተሰጥኦ ባሻገር፣ ከሞት አፍ ወጥቶ ለአርጀንቲና ማሊያ እስከመበቃት ያደረገውን ተአምራዊ ጉዞ የተመለከቱ የስፖርቱ ተከታታዮች፣ "እግር ኳስ ሰዎችን የሚያስተስርር ድንቅ ድልድይ ነው" ሲሉ አድናቆታቸውን ገልጸዋል።
ገና በ17 ዓመቱ በአርጀንቲና እግር ኳስ ታሪክ ውስጥ ልዩ ቦታ የያዘው ይህ ፈጣን የክንፍ መስመር ተጫዋች፣ በቀጣይ በታላቁ የአርጀንቲና ዋና ብሔራዊ ቡድን ውስጥ የመሰለፍ ህልሙን ያሳካ ይሆን? የዓለም እግር ኳስ አፍቃሪዎች ከወዲሁ የዚህን ድንቅ ወጣት ቀጣይ እርምጃዎች በትልቅ ጉጉት እየተከታተሉ ይገኛሉ።
የ17 ዓመቱ ስቲቨን "ኪኪ" ራሞስ ለአርጀንቲና ከ17 ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድን በመሰለፍ፣ በሄይቲ ተወልዶ የታላቋን ደቡብ አሜሪካ ሀገር ማሊያ የለበሰ የመጀመሪያው ተጫዋች መሆን ችሏል!
በታዋቂው የቬሌዝ ሳርስፊልድ አካዳሚ ውስጥ በክንፍ አጥቂነት የሚያበራው ይህ ታዳጊ፣ አርጀንቲና ኢኳዶርን 2ለ1 ባሸነፈችበት ጨዋታ ላይ ለአልቢሴሌስቴዎች የመጀመሪያ ጨዋታውን አድርጓል። በጨዋታው ላይ ድንቅ እንቅስቃሴ በማሳየት እና ሁለት ግቦችን በማስቆጠር ቡድኑን ለድል ያበቃው ኪኪ ራሞስ፣ በዓለም እግር ኳስ ግዙፍ ስም ባላቸው አርጀንቲናውያን ዘንድ ስሙን በወርቅ ቀለም ጽፏል።
በ2009 በፖርት-ኦ-ፕሪንስ ሄይቲ የተወለደው ኪኪ፣ ለአርጀንቲና በማንኛውም የዕድሜ እርከን ብሔራዊ ቡድን ውስጥ የተሰለፈ የመጀመሪያው በሄይቲ የተወለደ ጥቁር ተጫዋች በመሆን አዲስ የኢንተርናሽናል እግር ኳስ ምዕራፍ ከፍቷል።
የኪኪ የህይወት ታሪክ ልክ እንደ አስደናቂ የፊልም ስክሪፕት ነው። እ.ኤ.አ በ2010 በሄይቲ ደርሶ በነበረው አውዳሚ የመሬት መንቀጥቀጥ ወቅት ገና የ8 ወር ህጻን የነበረው ኪኪ፣ በነበረበት የሕፃናት ማደሪያ ጣቢያ ውስጥ ጉዳት ሳይደርስበት ከተረፉት በጣም ጥቂት ህጻናት አንዱ ነበር።
ባዮሎጂካል ወላጆቹ አርጀንቲናውያን ባይሆኑም፣ አንድ ደግ ልብ ያላቸው አርጀንቲናውያን ባልና ሚስት በጉዲፈቻ ወስደው ወደ ቦነስ አይረስ አመጡት። ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ህይወቱን ሙሉ በአርጀንቲና ያሳለፈው፣ ቋንቋውን እና ባህሉን ለምዶ ያደገው ኪኪ፣ የሀገሪቱን ዜግነት በመያዝ ለብሔራዊ ቡድኑ የመጫወት ህጋዊ መብትን አግኝቷል።
የኪኪ ራሞስ ታሪክ ይፋ መሆንን ተከትሎ በአርጀንቲናውያን የእግር ኳስ አፍቃሪዎች ዘንድ ከፍተኛ ደስታ እና ኩራት ተፈጥሯል። በጨዋታው ካሳየው ከፍተኛ ተሰጥኦ ባሻገር፣ ከሞት አፍ ወጥቶ ለአርጀንቲና ማሊያ እስከመበቃት ያደረገውን ተአምራዊ ጉዞ የተመለከቱ የስፖርቱ ተከታታዮች፣ "እግር ኳስ ሰዎችን የሚያስተስርር ድንቅ ድልድይ ነው" ሲሉ አድናቆታቸውን ገልጸዋል።
ገና በ17 ዓመቱ በአርጀንቲና እግር ኳስ ታሪክ ውስጥ ልዩ ቦታ የያዘው ይህ ፈጣን የክንፍ መስመር ተጫዋች፣ በቀጣይ በታላቁ የአርጀንቲና ዋና ብሔራዊ ቡድን ውስጥ የመሰለፍ ህልሙን ያሳካ ይሆን? የዓለም እግር ኳስ አፍቃሪዎች ከወዲሁ የዚህን ድንቅ ወጣት ቀጣይ እርምጃዎች በትልቅ ጉጉት እየተከታተሉ ይገኛሉ።
8 days ago
ሳዳም በስቅላት!
በኢራቅ ጅምላ ጨራሽ መሳሪያዎች አልተገኙም!
#ethiopia | እ.ኤ.አ. መጋቢት 20 ቀን 2003 አሜሪካ ከብሪታንያ እና ከሌሎች አጋሮቿ ጋር በመሆን በኢራቅ ላይ ድንገተኛ ወረራ ፈጸመች።
የወረራው ዋነኛ ምክንያት ሳዳም ሁሴን የጅምላ ጨራሽ መሣሪያዎች ባለቤት ናቸው ለዓለምም ስጋት ደቅነዋል የሚል ነበረ።
ይህንን ተከትሎ በባግዳድ ሰማይ ስር የተካሄደው ከባድ የቦምብ ድብደባ የብዙ ንጹሃንን ሕይወት የቀጠፈ ሲሆን መኖሪያ ቤቶች፣ ሆስፒታሎች፣ ትምህርት ቤቶች እና መሠረተ ልማቶች እንዲወድሙ ምክንያት ሆኗል።
በርካታ ቤተሰቦች ሲፈናቀሉ፣ ሕፃናት ተቀብረዋል አገሪቱም እስከዛሬ ድረስ ወደማያበቃ መከራና ውዥንብር ውስጥ ገብታለች።
ከወራት መሸሸግ በኋላ በታህሳስ 13 ቀን 2003 ሳዳም ሁሴን በተክሪት አቅራቢያ በአሜሪካ ጦር ከተያዙ በኋላ በጥቅምት 19 ቀን 2005 በባግዳድ በከፍተኛ ጥበቃ ሥር በሚገኘው የኢራቅ ከፍተኛ ችሎት ፍርድ ቤት ቀረቡ።
በሕዳር 5 ቀን 2006 በ1982 በዱጃይል ከተፈጸመው የሰዎች ግድያ ጋር ተያይዞ በሰብአዊነት ላይ በተፈጸመ ወንጀል ጥፋተኛ ተብለው በሞት እንዲቀጡ የተወሰነባቸው ሲሆን፣ በታህሳስ 30 ቀን 2006 ቅጣታቸው ስቅላት ሆኗል።
ሆኖም ለወረራውና ለተከተለው የሃያ ዓመታት መከራ መነሻ የተደረጉት የጅምላ ጨራሽ መሣሪያዎች በኢራቅ ምድር በጭራሽ ሳይገኙ ቀርተዋል።
በያፌት ገ/ህይወት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
በኢራቅ ጅምላ ጨራሽ መሳሪያዎች አልተገኙም!
#ethiopia | እ.ኤ.አ. መጋቢት 20 ቀን 2003 አሜሪካ ከብሪታንያ እና ከሌሎች አጋሮቿ ጋር በመሆን በኢራቅ ላይ ድንገተኛ ወረራ ፈጸመች።
የወረራው ዋነኛ ምክንያት ሳዳም ሁሴን የጅምላ ጨራሽ መሣሪያዎች ባለቤት ናቸው ለዓለምም ስጋት ደቅነዋል የሚል ነበረ።
ይህንን ተከትሎ በባግዳድ ሰማይ ስር የተካሄደው ከባድ የቦምብ ድብደባ የብዙ ንጹሃንን ሕይወት የቀጠፈ ሲሆን መኖሪያ ቤቶች፣ ሆስፒታሎች፣ ትምህርት ቤቶች እና መሠረተ ልማቶች እንዲወድሙ ምክንያት ሆኗል።
በርካታ ቤተሰቦች ሲፈናቀሉ፣ ሕፃናት ተቀብረዋል አገሪቱም እስከዛሬ ድረስ ወደማያበቃ መከራና ውዥንብር ውስጥ ገብታለች።
ከወራት መሸሸግ በኋላ በታህሳስ 13 ቀን 2003 ሳዳም ሁሴን በተክሪት አቅራቢያ በአሜሪካ ጦር ከተያዙ በኋላ በጥቅምት 19 ቀን 2005 በባግዳድ በከፍተኛ ጥበቃ ሥር በሚገኘው የኢራቅ ከፍተኛ ችሎት ፍርድ ቤት ቀረቡ።
በሕዳር 5 ቀን 2006 በ1982 በዱጃይል ከተፈጸመው የሰዎች ግድያ ጋር ተያይዞ በሰብአዊነት ላይ በተፈጸመ ወንጀል ጥፋተኛ ተብለው በሞት እንዲቀጡ የተወሰነባቸው ሲሆን፣ በታህሳስ 30 ቀን 2006 ቅጣታቸው ስቅላት ሆኗል።
ሆኖም ለወረራውና ለተከተለው የሃያ ዓመታት መከራ መነሻ የተደረጉት የጅምላ ጨራሽ መሣሪያዎች በኢራቅ ምድር በጭራሽ ሳይገኙ ቀርተዋል።
በያፌት ገ/ህይወት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
9 days ago
በምስራቅ አርሲ ዞን በታጣቂዎች የተፈጸሙ ከባድ የሰብዓዊ መብቶች ጥሰቶች ይፋ ሆኑ
#fastmereja I የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ጉባዔ (ኢሰመጉ) በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ አርሲ ዞን በተለያዩ ወረዳዎች ከ2014 ዓ.ም እስከ ግንቦት 2018 ዓ.ም ባለው ጊዜ ውስጥ በታጣቂ ቡድኖች በተፈጸሙ ጥቃቶች ላይ ያከናወነውን የምርመራ ግኝት የያዘ 158ኛ ልዩ መግለጫውን ይፋ አድርጓል። በዞኑ በሚገኙ ሽርካ፣ ሮቤ፣ ጀጁ፣ መርቲ፣ ጉና፣ ሆንቆሎ ዋቤ፣ አርሲ ሲሬ፣ ሙኒሳ እና አሰኮ ወረዳዎች በተፈጸሙት ጥቃቶች በሃይማኖትና ማንነት ላይ ያነጣጠሩ የሰዎች ግ ድያ፣ አካል ጉዳት፣ እገታ፣ መፈናቀል እና የንብረት ውድመት መከሰታቸው ተረጋገጧል።
ኢሰመጉ ከመጋቢት 3 እስከ 9 ቀን 2018 ዓ.ም ባደረገው የመስክ ምርመራና ከሟች ቤተሰቦች፣ ተጎጂዎች፣ የዓይን እማኞች እና የአርሲ ሀገረ ስብከት ቤተክህነት ጽሕፈት ቤቶች ባሰበሰባቸው መረጃዎች መሰረት በጥቃቱ በርካታ ንጹሃን ዜጎች ሕይወታቸውን አጥተዋል። ከ2014 ዓ.ም እስከ ግንቦት 24/2018 ዓ.ም ዓ.ም የተፈጸሙ የሰብዓዊ መብቶች ጥሰቶች የምርመራ ስራን አከናውኗል፡፡ በተሰበሰበው መረጃ መሰረት:-
📌 በሽርካ ወረዳ 116፣
📌 በመርቲ ወረዳ 117፣
📌 በጀጁ ወረዳ 101፣
📌 በሮቤ ወረዳ 47፣
📌 በጉና ወረዳ 26፣
📌 በሆንቆሎ ዋቤ ወረዳ 20፣
📌 በሙኒሳ ወረዳ 19፣
📌 በአሰኮ ወረዳ 5 ንጹሃን እና 4 የጸጥታ አካላት (ሚሊሻዎች) እንዲሁም
📌 በሲሬ ወረዳ 3 ሰዎች ተገ ድለዋል።
ከግድ ያው በተጨማሪ ከፍተኛ የእገታ ወንጀል የተፈጸመ ሲሆን፣
📍በሮቤ ወረዳ 156 ሰዎች፣
📍በጀጁ ወረዳ 182 ሰዎች፣
📍በመርቲ ወረዳ 29 ሰዎች
📍በሽርካ ወረዳ 39 ሰዎች ታግተው በርካቶቹ በካሳ ክፍያ የተለቀቁ ቢሆንም የበርካታ ታጋቾች የደረሱበት ሁኔታ እስከ አሁን አይታወቅም። እንዲሁም በሕፃናትና አዛውንቶች ላይ የቆሰሉና አካል ጉዳት የደረሰባቸው ሲሆን፣ በሺዎች የሚቆጠሩ ነዋሪዎች ከቀያቸው ተፈናቅለዋል። የአሰኮ ወረዳ የጠለታ ጨፋ ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያንን ጨምሮ በርካታ አብያተ ክርስቲያናት መዘረፋቸውና መቃጠላቸው፣ የመኖሪያ ቤቶች መፍረሳቸው እና የቀንድና የጋማ ከብቶች መዘረፋቸው በምርመራው ተረጋግጧል።
ኢሰመጉ መንግስት የዜጎችን በሕይወት የመኖርና የንብረት ጥበቃ የማድረግ ሕገ-መንግሥታዊ ግዴታውን እንዲወጣ፣ በጥሰቱ የተሳተፉ አካላት በሕግ እንዲጠየቁ እና ለተፈናቀሉት ዘላቂ መፍትሔ እንዲሰጥ ጥሪ አቅርቧል።
#fastmereja I የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ጉባዔ (ኢሰመጉ) በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ አርሲ ዞን በተለያዩ ወረዳዎች ከ2014 ዓ.ም እስከ ግንቦት 2018 ዓ.ም ባለው ጊዜ ውስጥ በታጣቂ ቡድኖች በተፈጸሙ ጥቃቶች ላይ ያከናወነውን የምርመራ ግኝት የያዘ 158ኛ ልዩ መግለጫውን ይፋ አድርጓል። በዞኑ በሚገኙ ሽርካ፣ ሮቤ፣ ጀጁ፣ መርቲ፣ ጉና፣ ሆንቆሎ ዋቤ፣ አርሲ ሲሬ፣ ሙኒሳ እና አሰኮ ወረዳዎች በተፈጸሙት ጥቃቶች በሃይማኖትና ማንነት ላይ ያነጣጠሩ የሰዎች ግ ድያ፣ አካል ጉዳት፣ እገታ፣ መፈናቀል እና የንብረት ውድመት መከሰታቸው ተረጋገጧል።
ኢሰመጉ ከመጋቢት 3 እስከ 9 ቀን 2018 ዓ.ም ባደረገው የመስክ ምርመራና ከሟች ቤተሰቦች፣ ተጎጂዎች፣ የዓይን እማኞች እና የአርሲ ሀገረ ስብከት ቤተክህነት ጽሕፈት ቤቶች ባሰበሰባቸው መረጃዎች መሰረት በጥቃቱ በርካታ ንጹሃን ዜጎች ሕይወታቸውን አጥተዋል። ከ2014 ዓ.ም እስከ ግንቦት 24/2018 ዓ.ም ዓ.ም የተፈጸሙ የሰብዓዊ መብቶች ጥሰቶች የምርመራ ስራን አከናውኗል፡፡ በተሰበሰበው መረጃ መሰረት:-
📌 በሽርካ ወረዳ 116፣
📌 በመርቲ ወረዳ 117፣
📌 በጀጁ ወረዳ 101፣
📌 በሮቤ ወረዳ 47፣
📌 በጉና ወረዳ 26፣
📌 በሆንቆሎ ዋቤ ወረዳ 20፣
📌 በሙኒሳ ወረዳ 19፣
📌 በአሰኮ ወረዳ 5 ንጹሃን እና 4 የጸጥታ አካላት (ሚሊሻዎች) እንዲሁም
📌 በሲሬ ወረዳ 3 ሰዎች ተገ ድለዋል።
ከግድ ያው በተጨማሪ ከፍተኛ የእገታ ወንጀል የተፈጸመ ሲሆን፣
📍በሮቤ ወረዳ 156 ሰዎች፣
📍በጀጁ ወረዳ 182 ሰዎች፣
📍በመርቲ ወረዳ 29 ሰዎች
📍በሽርካ ወረዳ 39 ሰዎች ታግተው በርካቶቹ በካሳ ክፍያ የተለቀቁ ቢሆንም የበርካታ ታጋቾች የደረሱበት ሁኔታ እስከ አሁን አይታወቅም። እንዲሁም በሕፃናትና አዛውንቶች ላይ የቆሰሉና አካል ጉዳት የደረሰባቸው ሲሆን፣ በሺዎች የሚቆጠሩ ነዋሪዎች ከቀያቸው ተፈናቅለዋል። የአሰኮ ወረዳ የጠለታ ጨፋ ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያንን ጨምሮ በርካታ አብያተ ክርስቲያናት መዘረፋቸውና መቃጠላቸው፣ የመኖሪያ ቤቶች መፍረሳቸው እና የቀንድና የጋማ ከብቶች መዘረፋቸው በምርመራው ተረጋግጧል።
ኢሰመጉ መንግስት የዜጎችን በሕይወት የመኖርና የንብረት ጥበቃ የማድረግ ሕገ-መንግሥታዊ ግዴታውን እንዲወጣ፣ በጥሰቱ የተሳተፉ አካላት በሕግ እንዲጠየቁ እና ለተፈናቀሉት ዘላቂ መፍትሔ እንዲሰጥ ጥሪ አቅርቧል።
10 days ago
ኬንያ እና ኢትዮጵያ እየተማማሩ ነው
#ethiopia | የኢትዮጵያ የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር ዶክተር ደረጀ ድጉማ የተመራ ከፍተኛ የልዑካን ቡድን ከኬንያ የሕዝብ ጤና እና ሙያዊ ደረጃዎች መምሪያ ዋና ጸሐፊ ሜሪ ሙቶኒ ጋር የምክክር ስብሰባ አካሄዱ።
የምክክር መድረኩ ዋና ዓላማ ኬንያ የእናቶችና ሕፃናትን ጤና ለማሻሻል በሰው ሰራሽ አስተዋጽኦ (AI) የታገዘ አልትራሳውንድ ቴክኖሎጂን (AI-POCUS) በመተግበር ረገድ ያካበተችውን ተሞክሮ ለኢትዮጵያ ማጋራት ነው።
በስብሰባው ወቅት ኬንያ በዲጂታል ጤና ፈጠራ፣ በመልካም አስተዳደር እና የኤአይ አልትራሳውንድ አገልግሎትን በማስፋፋት ረገድ ያስመዘገበችው እድገት የቀረበ ሲሆን ይህም ኢትዮጵያ ተመሳሳይ ቴክኖሎጂን በሀገር ውስጥ በመዘርጋት የእናቶችና ሕፃናትን ሕክምና ለማጠናከር ለምናደርገው ዝግጅት ትልቅ ጥቆማ የሚሰጥ ነው ተብሏል።
ይህ ውይይት ኢትዮጵያና ኬንያ በዲጂታል ጤና መፍትሔዎች፣ በእውቀት ሽግግር እና በቀጣናው ጠንካራ የጤና ስርዓት በመገንባት የእናቶችና ሕፃናትን የጤና ሁኔታ ለማሻሻል ያላቸውን አጋርነት ይበልጥ ለማጠናከር ያላቸውን ቁርጠኝነት ዳግም ያረጋገጡበት ሆኖ አልፏል።
በያፌት ገ/ህይወት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#ethiopia | የኢትዮጵያ የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር ዶክተር ደረጀ ድጉማ የተመራ ከፍተኛ የልዑካን ቡድን ከኬንያ የሕዝብ ጤና እና ሙያዊ ደረጃዎች መምሪያ ዋና ጸሐፊ ሜሪ ሙቶኒ ጋር የምክክር ስብሰባ አካሄዱ።
የምክክር መድረኩ ዋና ዓላማ ኬንያ የእናቶችና ሕፃናትን ጤና ለማሻሻል በሰው ሰራሽ አስተዋጽኦ (AI) የታገዘ አልትራሳውንድ ቴክኖሎጂን (AI-POCUS) በመተግበር ረገድ ያካበተችውን ተሞክሮ ለኢትዮጵያ ማጋራት ነው።
በስብሰባው ወቅት ኬንያ በዲጂታል ጤና ፈጠራ፣ በመልካም አስተዳደር እና የኤአይ አልትራሳውንድ አገልግሎትን በማስፋፋት ረገድ ያስመዘገበችው እድገት የቀረበ ሲሆን ይህም ኢትዮጵያ ተመሳሳይ ቴክኖሎጂን በሀገር ውስጥ በመዘርጋት የእናቶችና ሕፃናትን ሕክምና ለማጠናከር ለምናደርገው ዝግጅት ትልቅ ጥቆማ የሚሰጥ ነው ተብሏል።
ይህ ውይይት ኢትዮጵያና ኬንያ በዲጂታል ጤና መፍትሔዎች፣ በእውቀት ሽግግር እና በቀጣናው ጠንካራ የጤና ስርዓት በመገንባት የእናቶችና ሕፃናትን የጤና ሁኔታ ለማሻሻል ያላቸውን አጋርነት ይበልጥ ለማጠናከር ያላቸውን ቁርጠኝነት ዳግም ያረጋገጡበት ሆኖ አልፏል።
በያፌት ገ/ህይወት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
10 days ago
በማዕከላዊ ጎንደር ዞን የሚገኘው ታሪካዊው የሙት አንሳ ማር ቅዱስ ሚካኤል አንድነት ገዳም የልማት ስራዎች ተጎበኙ
በማዕከላዊ ጎንደር ዞን በምስራቅ በለሳ የሚገኘው የሙት አንሳ ማር ቅዱስ ሚካኤል አንድነት ገዳም የመሰረተ ልማት እና የአካባቢ ጥበቃ ፕሮጀክት የመጀመሪያ ምዕራፍ ግንባታ ተጎበኘ።
ይህ ግዙፍ ፕሮጀክት በ2015 ዓ.ም. በመስክ ጥናትና በህጋዊነት ማረጋገጫ ተጀምሮ፣ ጥር 2016 ዓ.ም. መሰረት ድንጋይ ከተጣለ በኋላ በ133 የሥራ ቀናት ውስጥ የመጀመሪያው ምዕራፍ ጥር 2017 ዓ.ም ተጠናቋል።
📍የመጀመሪያው ምዕራፍ አበይት ስኬቶች፦
📌 የመነኮሳት በዓታት
4 መነኮሳትን በጋራ ማስተናገድ የሚችሉ 19 ክፍሎች (እያንዳንዱ 12 ካሬ ሜትር) ተገንብተዋል። ክፍሎቹ ሙሉ መንፈሳዊ መጻሕፍት (መጽሐፍ ቅዱስ፣ ድርሳነ ሚካኤል፣ አርጋኖን) የተሟሉላቸው ናቸው።
📌 የአካባቢ ጥበቃና ልማት
የመሬት መንሸራተትን ለመከላከል ከ2 ሜትር በላይ ጥልቀት ያላቸው የጋቢዮን ግንባታዎች የተሰሩ ሲሆን፣ ከባህር ዳር እና ከሌሎች አካባቢዎች የተጓጓዙ የዛፍ ችግኞች በግቢው ውስጥ ተተክለዋል።
📌 የእጅ ስራ ማዕከል (ሸማ ቤት)
መነኮሳቱ የራሳቸውን አልባሳትና የገዳሙን ፍላጎት በራሳቸው አቅም እንዲሸፍኑ የሚያስችል የሸማ መስሪያ ማዕከልና መጋዘን ተገንብቷል። የተመረቱ ምርቶች ለገበያ እየቀረቡ ይገኛሉ።
📌የመንገድና መሰረተ ልማት
6 ሜትር ስፋት ያለው 8 ኪሎ ሜትር የጥርጊያ መንገድ፣ 170 ሜትር የድንጋይ ንጣፍ መንገድ እና ወደ ጸበል ቦታ የሚወስድ የድንጋይ ንጣፍ ደረጃ ተሰርቷል።
📌 በሶላር መብራት ተገጥሞ በግቢው ውስጥ እና በክፍሎች ውስጥ አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል።
📌ቁሳቁስና እንስሳት
ለአገልግሎትና ለጭነት የሚሆኑ በቅሎዎች፣ አህዮች፣ ከብቶች፣ በጎችና ፍየሎች ተገዝተዋል።
ያጋጠሙ ፈተናዎች፦
የፀጥታ ስጋት፣ የመሰረተ ልማት አለመኖር እና የመንገድ መዘጋት ዋና ዋና ማነቆዎች ነበሩ። ቡድኑ ቁሳቁስ ለማጓጓዝ ከመካከለኛው ጎንደር ተነስቶ በደቡብ ጎንደር በኩል ረጅም መንገድ ለመዞር ተገዷል። በተጨማሪም በወር እስከ 15 ቀናት አካባቢ በሃይማኖታዊ ስርዓት ምክንያት ስራ የሚቆም ቢሆንም፣ ፕሮጀክቱ በተቀመጠለት ጊዜ ተጠናቋል።
🏗️ የሁለተኛው ምዕራፍ እንቅስቃሴ (ከህዳር 2018 ዓ.ም. ጀምሮ)፦
📌 በ1,300 ካሬ ሜትር ላይ ያረፈው የቤተክርስቲያኑ የፋውንዴሽን እና የአፈር ሙላት ስራ ተጠናቆ ለጣራና ለግድግዳ ስራ ዝግጁ ሆኗል።
📌 5 ክፍሎች ያሉት የጳጳሳትና የእንግዶች ማረፊያ ህንጻ ግንባታ እየተጠናቀቀ ይገኛል።
📌 የቤተክርስቲያኑ ግንባታ ብቻ እስከ 30 ሚሊዮን ብር ወጪ የሚጠይቅ ሲሆን፣ ሙሉ ፕሮጀክቱ ከተያዘለት 3 ዓመት ከ6 ወር ቀድሞ በ2 ዓመት ውስጥ ይጠናቀቃል ተብሎ ይጠበቃል።
📌 የመነኮሳት መኖሪያ
በተከናወነው የህንፃ ግንባታ መርሃ-ግብር ለእናቶች (መነኮሳት) ቅድሚያ ተሰጥቶ አጠቃላይ የማረፊያ ክፍሎች ግንባታ ተጠናቋል።
በሁለተኛው ምዕራፍ ግንባታ የአባት መነኮሳት መኖሪያ እያንዳንዱ ክፍል 12 ካሬ ሜትር ስፋት ያለውና እስከ 4 መነኮሳትን ማስተናገድ በሚያስችል መልኩ የተቃኘ ነው። በተጨማሪም 18 ካሬ ሜትር ስፋት ያላቸው ክፍሎች ከተለያዩ ገዳማት ለልምድ ልውውጥና ለመንፈሳዊ አገልግሎት ለሚመጡ እንግዳ መነኮሳት ማረፊያነት የተዘጋጁ ናቸው። በአጠቃላይ መኖሪያው እስከ 64 አባቶችን የመያዝ አቅም አለው። በሚቀጥሉት 1 ወር ባለው ጊዜ የማጠናቀቂያ ስራዎች ተሰርተው ይጠናቀቃል ተብሎ ይጠበቃል።
ገዳሙ በሰው እጅ ሳይጠበቅ በራሱ የኢኮኖሚ አቅም መቆም የሚያስችለውን መሰረት ለመጣል ባለው የማምረቻ ሼድ ውስጥ ዘመናዊ የእንጨት፣ የብረትና የጥገና ስራዎች ተጀምረዋል። በዚህ ማምረቻ ውስጥ መነኮሳቱና ሰራተኞቹ በራሳቸው አቅም የደጃፍ በሮችን፣ የብረት ስራዎችን እንዲሁም የፎጣና የሽመና ምርቶችን ማምረትና መጠገን የሚያስችላቸው ስልጠናና የስራ አካባቢ ተመቻችቶላቸዋል። ይህም ገዳሙ በምግብና በቁሳቁስ ራሱን እንዲችል ትልቅ አስተዋፅኦ ያበረክታል።
የማዕድ ቤትና የሊቃውንት ማደሪያ
አጋፔ ማዕድ፦ መነኮሳቱና የመስክ ሰራተኞቹ በአንድነት ተሰብስበው ጸሎት ካደረጉ በኋላ በማህበር ማዕድ የሚቀምሱበት ሰፊ አዳራሽ ተገንብቶ ዝግጁ ሆኗል።
የሊቃውንት ማደሪያ፦ 9 ዘመናዊ ክፍሎችን ያካተተ ህንፃ የተገነባ ሲሆን፣ ካህናት፣ ዲያቆናትና አርድእት በተለየ ሁኔታ የሚያርፉበት ነው። የኤሌክትሪክ መስመር ዝርጋታ፣ የመጸዳጃና የሻወር ቤቶች ግንባታ እየተሰራ ይገኛል።
የቀጣይ ምዕራፍና የጸበል ቦታዎች ዕቅድ
ለጸበልተኞች፣ ለሱባዔተኞች፣ ለነፍሰ ጡሮች፣ ለሕፃናት እና ልዩ ትኩረት ለሚሹ (እንደ የስኳርና የኤች.አይ.ቪ መድኃኒት ለሚወስዱ) ታካሚዎች ምቹ የሆኑ የጸበልና የመጠለያ ቦታዎች፣ የሎከር እና የምግብ አቅርቦት አገልግሎቶች በዲዛይን ተካተዋል።
⚠️ የዋጋ ንረትና የትራንስፖርት ተጽዕኖ፦
የገበያ ዋጋ እና የትራንስፖርት ወጪ በከፍተኛ ሁኔታ ጨምሯል። ቀደም ሲል በአንድ የጭነት መኪና እስከ 38 ሺህ ብር የነበረው የጠጠር ማጓጓዣ ወጪ አሁን እስከ 100 ሺህ እና 110 ሺህ ብር ደርሷል። በተጨማሪም ቁሳቁስ ከአዲስ አበባ እና ከሌሎች አካባቢዎች ለማድረስ የነዳጅ እጥረትና የመንገድ ጥገና ታክሎበት ከ2 እስከ 5 ቀናት ይወስዳል ይህም የትራንስፖርት ወጪ በከፍተኛ ሁኔታ እንዲጨምር አድርጎታል።
በቀጣይ ክፍል የሙት አንሳ ማር ቅዱስ ሚካኤል አንድነት ገዳም በዙ ሀሙሲት ከተማ እየተሰሩ የልማት ስራዎች ይዘን እንቀርባለን።
ይቀጥላል...
ፎቶ ከበደ መክብብ
በማዕከላዊ ጎንደር ዞን በምስራቅ በለሳ የሚገኘው የሙት አንሳ ማር ቅዱስ ሚካኤል አንድነት ገዳም የመሰረተ ልማት እና የአካባቢ ጥበቃ ፕሮጀክት የመጀመሪያ ምዕራፍ ግንባታ ተጎበኘ።
ይህ ግዙፍ ፕሮጀክት በ2015 ዓ.ም. በመስክ ጥናትና በህጋዊነት ማረጋገጫ ተጀምሮ፣ ጥር 2016 ዓ.ም. መሰረት ድንጋይ ከተጣለ በኋላ በ133 የሥራ ቀናት ውስጥ የመጀመሪያው ምዕራፍ ጥር 2017 ዓ.ም ተጠናቋል።
📍የመጀመሪያው ምዕራፍ አበይት ስኬቶች፦
📌 የመነኮሳት በዓታት
4 መነኮሳትን በጋራ ማስተናገድ የሚችሉ 19 ክፍሎች (እያንዳንዱ 12 ካሬ ሜትር) ተገንብተዋል። ክፍሎቹ ሙሉ መንፈሳዊ መጻሕፍት (መጽሐፍ ቅዱስ፣ ድርሳነ ሚካኤል፣ አርጋኖን) የተሟሉላቸው ናቸው።
📌 የአካባቢ ጥበቃና ልማት
የመሬት መንሸራተትን ለመከላከል ከ2 ሜትር በላይ ጥልቀት ያላቸው የጋቢዮን ግንባታዎች የተሰሩ ሲሆን፣ ከባህር ዳር እና ከሌሎች አካባቢዎች የተጓጓዙ የዛፍ ችግኞች በግቢው ውስጥ ተተክለዋል።
📌 የእጅ ስራ ማዕከል (ሸማ ቤት)
መነኮሳቱ የራሳቸውን አልባሳትና የገዳሙን ፍላጎት በራሳቸው አቅም እንዲሸፍኑ የሚያስችል የሸማ መስሪያ ማዕከልና መጋዘን ተገንብቷል። የተመረቱ ምርቶች ለገበያ እየቀረቡ ይገኛሉ።
📌የመንገድና መሰረተ ልማት
6 ሜትር ስፋት ያለው 8 ኪሎ ሜትር የጥርጊያ መንገድ፣ 170 ሜትር የድንጋይ ንጣፍ መንገድ እና ወደ ጸበል ቦታ የሚወስድ የድንጋይ ንጣፍ ደረጃ ተሰርቷል።
📌 በሶላር መብራት ተገጥሞ በግቢው ውስጥ እና በክፍሎች ውስጥ አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል።
📌ቁሳቁስና እንስሳት
ለአገልግሎትና ለጭነት የሚሆኑ በቅሎዎች፣ አህዮች፣ ከብቶች፣ በጎችና ፍየሎች ተገዝተዋል።
ያጋጠሙ ፈተናዎች፦
የፀጥታ ስጋት፣ የመሰረተ ልማት አለመኖር እና የመንገድ መዘጋት ዋና ዋና ማነቆዎች ነበሩ። ቡድኑ ቁሳቁስ ለማጓጓዝ ከመካከለኛው ጎንደር ተነስቶ በደቡብ ጎንደር በኩል ረጅም መንገድ ለመዞር ተገዷል። በተጨማሪም በወር እስከ 15 ቀናት አካባቢ በሃይማኖታዊ ስርዓት ምክንያት ስራ የሚቆም ቢሆንም፣ ፕሮጀክቱ በተቀመጠለት ጊዜ ተጠናቋል።
🏗️ የሁለተኛው ምዕራፍ እንቅስቃሴ (ከህዳር 2018 ዓ.ም. ጀምሮ)፦
📌 በ1,300 ካሬ ሜትር ላይ ያረፈው የቤተክርስቲያኑ የፋውንዴሽን እና የአፈር ሙላት ስራ ተጠናቆ ለጣራና ለግድግዳ ስራ ዝግጁ ሆኗል።
📌 5 ክፍሎች ያሉት የጳጳሳትና የእንግዶች ማረፊያ ህንጻ ግንባታ እየተጠናቀቀ ይገኛል።
📌 የቤተክርስቲያኑ ግንባታ ብቻ እስከ 30 ሚሊዮን ብር ወጪ የሚጠይቅ ሲሆን፣ ሙሉ ፕሮጀክቱ ከተያዘለት 3 ዓመት ከ6 ወር ቀድሞ በ2 ዓመት ውስጥ ይጠናቀቃል ተብሎ ይጠበቃል።
📌 የመነኮሳት መኖሪያ
በተከናወነው የህንፃ ግንባታ መርሃ-ግብር ለእናቶች (መነኮሳት) ቅድሚያ ተሰጥቶ አጠቃላይ የማረፊያ ክፍሎች ግንባታ ተጠናቋል።
በሁለተኛው ምዕራፍ ግንባታ የአባት መነኮሳት መኖሪያ እያንዳንዱ ክፍል 12 ካሬ ሜትር ስፋት ያለውና እስከ 4 መነኮሳትን ማስተናገድ በሚያስችል መልኩ የተቃኘ ነው። በተጨማሪም 18 ካሬ ሜትር ስፋት ያላቸው ክፍሎች ከተለያዩ ገዳማት ለልምድ ልውውጥና ለመንፈሳዊ አገልግሎት ለሚመጡ እንግዳ መነኮሳት ማረፊያነት የተዘጋጁ ናቸው። በአጠቃላይ መኖሪያው እስከ 64 አባቶችን የመያዝ አቅም አለው። በሚቀጥሉት 1 ወር ባለው ጊዜ የማጠናቀቂያ ስራዎች ተሰርተው ይጠናቀቃል ተብሎ ይጠበቃል።
ገዳሙ በሰው እጅ ሳይጠበቅ በራሱ የኢኮኖሚ አቅም መቆም የሚያስችለውን መሰረት ለመጣል ባለው የማምረቻ ሼድ ውስጥ ዘመናዊ የእንጨት፣ የብረትና የጥገና ስራዎች ተጀምረዋል። በዚህ ማምረቻ ውስጥ መነኮሳቱና ሰራተኞቹ በራሳቸው አቅም የደጃፍ በሮችን፣ የብረት ስራዎችን እንዲሁም የፎጣና የሽመና ምርቶችን ማምረትና መጠገን የሚያስችላቸው ስልጠናና የስራ አካባቢ ተመቻችቶላቸዋል። ይህም ገዳሙ በምግብና በቁሳቁስ ራሱን እንዲችል ትልቅ አስተዋፅኦ ያበረክታል።
የማዕድ ቤትና የሊቃውንት ማደሪያ
አጋፔ ማዕድ፦ መነኮሳቱና የመስክ ሰራተኞቹ በአንድነት ተሰብስበው ጸሎት ካደረጉ በኋላ በማህበር ማዕድ የሚቀምሱበት ሰፊ አዳራሽ ተገንብቶ ዝግጁ ሆኗል።
የሊቃውንት ማደሪያ፦ 9 ዘመናዊ ክፍሎችን ያካተተ ህንፃ የተገነባ ሲሆን፣ ካህናት፣ ዲያቆናትና አርድእት በተለየ ሁኔታ የሚያርፉበት ነው። የኤሌክትሪክ መስመር ዝርጋታ፣ የመጸዳጃና የሻወር ቤቶች ግንባታ እየተሰራ ይገኛል።
የቀጣይ ምዕራፍና የጸበል ቦታዎች ዕቅድ
ለጸበልተኞች፣ ለሱባዔተኞች፣ ለነፍሰ ጡሮች፣ ለሕፃናት እና ልዩ ትኩረት ለሚሹ (እንደ የስኳርና የኤች.አይ.ቪ መድኃኒት ለሚወስዱ) ታካሚዎች ምቹ የሆኑ የጸበልና የመጠለያ ቦታዎች፣ የሎከር እና የምግብ አቅርቦት አገልግሎቶች በዲዛይን ተካተዋል።
⚠️ የዋጋ ንረትና የትራንስፖርት ተጽዕኖ፦
የገበያ ዋጋ እና የትራንስፖርት ወጪ በከፍተኛ ሁኔታ ጨምሯል። ቀደም ሲል በአንድ የጭነት መኪና እስከ 38 ሺህ ብር የነበረው የጠጠር ማጓጓዣ ወጪ አሁን እስከ 100 ሺህ እና 110 ሺህ ብር ደርሷል። በተጨማሪም ቁሳቁስ ከአዲስ አበባ እና ከሌሎች አካባቢዎች ለማድረስ የነዳጅ እጥረትና የመንገድ ጥገና ታክሎበት ከ2 እስከ 5 ቀናት ይወስዳል ይህም የትራንስፖርት ወጪ በከፍተኛ ሁኔታ እንዲጨምር አድርጎታል።
በቀጣይ ክፍል የሙት አንሳ ማር ቅዱስ ሚካኤል አንድነት ገዳም በዙ ሀሙሲት ከተማ እየተሰሩ የልማት ስራዎች ይዘን እንቀርባለን።
ይቀጥላል...
ፎቶ ከበደ መክብብ
10 days ago
ባሳለፍነው የፈረንጆቹ 2025 አመት ላይ 1.3 ሚሊዮን ሰዎች የጉበት በሽታ እንዳለባቸው ሳያውቁ ህይወታቸው ማለፉ ተነገረ።
#ethiopia | በዓለም ዙሪያ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎችን ሕይወት አደጋ ላይ የጣለውና ዝምተኛ ገዳይ በመባል የሚጠራው የሄፓታይቲስ የጉበት በሽታ ስርጭት ከፍተኛ ደረጃ መድረሱ የአለም ጤና ድርጅት ተናግሯል።
የዓለም ጤና ድርጅት ይፋ ባደረገው መረጃ መሠረት 287 ሚሊዮን የሚሆን የዓለም ሕዝብ በከባድ የሄፓታይቲስ "ቢ" እና "ሲ" ቫይረሶች ተይዞ ይገኛል ብሏል።
ሆኖም ግን ከእነዚህ መካከል አብዛኞቹ በደማቸው ውስጥ ቫይረሱ መኖሩን እንኳ እንደማያውቁ ነው የገለፀው።
በሽታው አስቀድሞ መከላከልና መታከም እንዲሁም ሙሉ በሙሉ መዳን የሚችል ቢሆንም ባለፈው ዓመት ብቻ 1.3 ሚሊዮን ሰዎች በዚሁ በሽታ ምክንያት ሕይወታቸውን ማጣታቸውን ገልጿል።
በፈረንጆቹ 2024 በአለም ዙርያ ከተወለዱ ህፃናት መካከል 45 በመቶ የሚሆኑት ብቻ ናቸው በተወለዱ በ24 ሰዓታት ውስጥ የመጀመሪያ የሄፓታይቲስ "ቢ" ክትባት ያገኙት ቀሪዎቹ አላገኙም ብሏል።
የአለም ጤና ድርጅት በየአመቱ ሃምሌ 21 ቀን የሚያከብረው ዓለም አቀፍ የጉበት በሽታ ቀን በነገው እለት እንደሚከበር ገልጿል።
አዲስ የሚወለዱ ሕፃናት በተወለዱ በ24 ሰዓታት ውስጥ የመጀመርያ ደረጃ ክትባት ማግኘታቸውን ማረጋገጥ እንደሚያስፈልጋ ድርጅቱ አስታውቋል።
ማንኛውም ሰው ቀደም ብሎ በሽታው ተመርምሮ የማያውቅ ከሆነ ወይም ለአደጋው ተጋላጭ ከሆነ አሁኑኑ የሄፓታይቲስ "ቢ" እና "ሲ" ምርመራ እንዲያደርግ አሳስቧል።
ሔኖክ ወ/ገብርኤል
#ethiopia #getutemesgen #getunews #who #worldhepatitisday #vaccine
#ethiopia | በዓለም ዙሪያ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎችን ሕይወት አደጋ ላይ የጣለውና ዝምተኛ ገዳይ በመባል የሚጠራው የሄፓታይቲስ የጉበት በሽታ ስርጭት ከፍተኛ ደረጃ መድረሱ የአለም ጤና ድርጅት ተናግሯል።
የዓለም ጤና ድርጅት ይፋ ባደረገው መረጃ መሠረት 287 ሚሊዮን የሚሆን የዓለም ሕዝብ በከባድ የሄፓታይቲስ "ቢ" እና "ሲ" ቫይረሶች ተይዞ ይገኛል ብሏል።
ሆኖም ግን ከእነዚህ መካከል አብዛኞቹ በደማቸው ውስጥ ቫይረሱ መኖሩን እንኳ እንደማያውቁ ነው የገለፀው።
በሽታው አስቀድሞ መከላከልና መታከም እንዲሁም ሙሉ በሙሉ መዳን የሚችል ቢሆንም ባለፈው ዓመት ብቻ 1.3 ሚሊዮን ሰዎች በዚሁ በሽታ ምክንያት ሕይወታቸውን ማጣታቸውን ገልጿል።
በፈረንጆቹ 2024 በአለም ዙርያ ከተወለዱ ህፃናት መካከል 45 በመቶ የሚሆኑት ብቻ ናቸው በተወለዱ በ24 ሰዓታት ውስጥ የመጀመሪያ የሄፓታይቲስ "ቢ" ክትባት ያገኙት ቀሪዎቹ አላገኙም ብሏል።
የአለም ጤና ድርጅት በየአመቱ ሃምሌ 21 ቀን የሚያከብረው ዓለም አቀፍ የጉበት በሽታ ቀን በነገው እለት እንደሚከበር ገልጿል።
አዲስ የሚወለዱ ሕፃናት በተወለዱ በ24 ሰዓታት ውስጥ የመጀመርያ ደረጃ ክትባት ማግኘታቸውን ማረጋገጥ እንደሚያስፈልጋ ድርጅቱ አስታውቋል።
ማንኛውም ሰው ቀደም ብሎ በሽታው ተመርምሮ የማያውቅ ከሆነ ወይም ለአደጋው ተጋላጭ ከሆነ አሁኑኑ የሄፓታይቲስ "ቢ" እና "ሲ" ምርመራ እንዲያደርግ አሳስቧል።
ሔኖክ ወ/ገብርኤል
#ethiopia #getutemesgen #getunews #who #worldhepatitisday #vaccine
Sponsored by
Surafel
11 days ago
በኢትዮጵያ በመጪዎቹ ዓመታት ሥራ አጥነት ፈታኝ እንደሚሆን የዓለም የሥራ ድርጅት ገለጸ
የዜጎች ማኅበራዊ ጥበቃ አገልግሎት እንዲጨምር ጠይቋል
በትምህርት ያልገፉና የሥራ ልምድ የሌላቸው ወጣቶች በክህሎት ማነስና በራሳቸው ሥራ ለመጀመር በሚገጥማቸው የፋይናንስ ችግር የሥራ ዕድል ዕጦት እንደሚያጋጥማቸው፣ የዓለም የሥራ ድርጅት (ILO) ገለጸ፡፡
የዓለም የሥራ ድርጅት ከሴቶችና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ ከዩናይትድ ኪንግደም ተራድኦ ድርጅት (ዩኤአይድ) እና ከሌሎች ተቋማት በጋራ በመሆን፣ በማኅበራዊ ጥበቃ ላይ ያዘጋጀውን ሪፖርት ይፋ ሲያደርግ ነው ይህንን የገለጸው፡፡በሪፖርቱ መሠረት ቁጥራቸው እያደገ ያለው ሥራ ፈላጊ ወጣቶች፣ በክህሎት ክፍተትና የራስን ቢዝነስ ለመጀመር በሚገጥማቸው የፋይናንስ ዕጦት ከፍተኛ ተግዳሮት ይገጥማቸዋል፡፡
የሕፃናት ቁጥር በከፍተኛ ሁኔታ መጨመር ወደ ሥራ ሊገባ የሚገባውን የወጣት ቁጥር የሚያሳድገው በመሆኑ፣ ዕድገቱን ከከተሞች የሥራ ገበያ ዕድል ጋር አጣጥሞና አዋህዶ መሄድ ከፍተኛ ፈተና ይሆናል ብሏል፡፡
በአገር አቀፍ ደረጃ የአካል ጉዳተኞች ቁጥር 17.6 በመቶ እንደሚደርስ ጠቅሶ፣ አካታችና ሁሉን አቀፍ የኢኮኖሚና የማኅበራዊ ተሳትፎን የሚደግፉ ፖሊሲዎችና መሠረተ ልማቶችን ማስፋፋት እንደሚያስፈልግ ገልጿል፡፡
በአገር አቀፍ ደረጃ ለሥራ ብቁ የሆነው የሕዝብ ቁጥር እ.ኤ.አ. በ2015 ከነበረበት 54.7 ሚሊዮን እ.ኤ.አ. በ2025 74.8 ሚሊዮን፣ እ.ኤ.አ. በ2030 ወደ 85.3 እንደሚደርስ ሪፖርቱ ያመለክታል፡፡
Seledadotio
Seledadotio
የዜጎች ማኅበራዊ ጥበቃ አገልግሎት እንዲጨምር ጠይቋል
በትምህርት ያልገፉና የሥራ ልምድ የሌላቸው ወጣቶች በክህሎት ማነስና በራሳቸው ሥራ ለመጀመር በሚገጥማቸው የፋይናንስ ችግር የሥራ ዕድል ዕጦት እንደሚያጋጥማቸው፣ የዓለም የሥራ ድርጅት (ILO) ገለጸ፡፡
የዓለም የሥራ ድርጅት ከሴቶችና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ ከዩናይትድ ኪንግደም ተራድኦ ድርጅት (ዩኤአይድ) እና ከሌሎች ተቋማት በጋራ በመሆን፣ በማኅበራዊ ጥበቃ ላይ ያዘጋጀውን ሪፖርት ይፋ ሲያደርግ ነው ይህንን የገለጸው፡፡በሪፖርቱ መሠረት ቁጥራቸው እያደገ ያለው ሥራ ፈላጊ ወጣቶች፣ በክህሎት ክፍተትና የራስን ቢዝነስ ለመጀመር በሚገጥማቸው የፋይናንስ ዕጦት ከፍተኛ ተግዳሮት ይገጥማቸዋል፡፡
የሕፃናት ቁጥር በከፍተኛ ሁኔታ መጨመር ወደ ሥራ ሊገባ የሚገባውን የወጣት ቁጥር የሚያሳድገው በመሆኑ፣ ዕድገቱን ከከተሞች የሥራ ገበያ ዕድል ጋር አጣጥሞና አዋህዶ መሄድ ከፍተኛ ፈተና ይሆናል ብሏል፡፡
በአገር አቀፍ ደረጃ የአካል ጉዳተኞች ቁጥር 17.6 በመቶ እንደሚደርስ ጠቅሶ፣ አካታችና ሁሉን አቀፍ የኢኮኖሚና የማኅበራዊ ተሳትፎን የሚደግፉ ፖሊሲዎችና መሠረተ ልማቶችን ማስፋፋት እንደሚያስፈልግ ገልጿል፡፡
በአገር አቀፍ ደረጃ ለሥራ ብቁ የሆነው የሕዝብ ቁጥር እ.ኤ.አ. በ2015 ከነበረበት 54.7 ሚሊዮን እ.ኤ.አ. በ2025 74.8 ሚሊዮን፣ እ.ኤ.አ. በ2030 ወደ 85.3 እንደሚደርስ ሪፖርቱ ያመለክታል፡፡
Seledadotio
Seledadotio
12 days ago
ሕፃናትን በማታለል የደፈሩ ጥበቃ በ25 ዓመት ጽኑ እስራት ተቀጡ
#ethiopia | በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል፣ በዎላይታ ዞን ቦዲቲ ከተማ ሶዶ በር ቀበሌ በሚገኘው የንጋት ትምህርት ቤት ጥበቃ ሆኖ የሚሠሩት ታዲዎስ ሞታ የተባለ ግለሰብ፣ የ5 እና 7 ዓመት ሕፃናት ላይ ግብረ-ሥጋ ድፍረት በመፈጸማቸው የ25 ዓመት ጽኑ እስራት ቅጣት ተጣለባቸው።
ተከሳሹ ሰኔ 27 ቀን 2018 ዓ.ም. ሕፃናቱን “ዥዋዥዌ ትጫወታላችሁ” በማለት በማታለል በሚሠሩበት ትምህርት ቤት ግቢ ውስጥ ወደሚገኝ ማደሪያ ክፍል በማስገባት ወንጀሉን ፈጽመዋል።
ፖሊስ በሰበሰበው ማስረጃ ድርጊቱ መፈጸሙን ማረጋገጥ ተችሏል።
ጉዳዩን ሲመረምር የቆየው የቦዲቲ ከተማ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ሐምሌ 17 ቀን 2018 ዓ.ም. በዋለው ችሎት፣ ዐቃቤ ሕግ ያቀረበውን ማስረጃ ከመረመረ በኋላ ተከሳሹ በኢ.ፌ.ዲ.ሪ. የወንጀል ሕግ አንቀጽ 60/ሀ እና 627/1 መሠረት ጥፋተኛ መሆኑን አረጋግጧል።
ፍርድ ቤቱ ተከሳሹን እንዲሁም መሰል ወንጀል ፈጻሚዎችን ለማስተማርና ለመከላከል በሚል የ25 ዓመት ጽኑ እስራት ቅጣት ወስኖበባቸዋል።
የቦዲቲ ከተማ ኮሚኒኬሽን ጽሕፈት ቤት
#ethiopia | በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል፣ በዎላይታ ዞን ቦዲቲ ከተማ ሶዶ በር ቀበሌ በሚገኘው የንጋት ትምህርት ቤት ጥበቃ ሆኖ የሚሠሩት ታዲዎስ ሞታ የተባለ ግለሰብ፣ የ5 እና 7 ዓመት ሕፃናት ላይ ግብረ-ሥጋ ድፍረት በመፈጸማቸው የ25 ዓመት ጽኑ እስራት ቅጣት ተጣለባቸው።
ተከሳሹ ሰኔ 27 ቀን 2018 ዓ.ም. ሕፃናቱን “ዥዋዥዌ ትጫወታላችሁ” በማለት በማታለል በሚሠሩበት ትምህርት ቤት ግቢ ውስጥ ወደሚገኝ ማደሪያ ክፍል በማስገባት ወንጀሉን ፈጽመዋል።
ፖሊስ በሰበሰበው ማስረጃ ድርጊቱ መፈጸሙን ማረጋገጥ ተችሏል።
ጉዳዩን ሲመረምር የቆየው የቦዲቲ ከተማ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ሐምሌ 17 ቀን 2018 ዓ.ም. በዋለው ችሎት፣ ዐቃቤ ሕግ ያቀረበውን ማስረጃ ከመረመረ በኋላ ተከሳሹ በኢ.ፌ.ዲ.ሪ. የወንጀል ሕግ አንቀጽ 60/ሀ እና 627/1 መሠረት ጥፋተኛ መሆኑን አረጋግጧል።
ፍርድ ቤቱ ተከሳሹን እንዲሁም መሰል ወንጀል ፈጻሚዎችን ለማስተማርና ለመከላከል በሚል የ25 ዓመት ጽኑ እስራት ቅጣት ወስኖበባቸዋል።
የቦዲቲ ከተማ ኮሚኒኬሽን ጽሕፈት ቤት
13 days ago
"ታሪክ ይፈርዳል ሕዝብ ይመሰክራል እውነት ለዘላለም ይኖራል!"
#ethiopia | እኔ ለኢትዮጵያ የተወለድሁ በኢትዮጵያ ያደግሁ ለኢትዮጵያም ሕይወቴን ለመስጠት በቃልኪዳን የቆምኩ ኩሩ ወታደር ነበርኩ ።
ወታደርነት ዩኒፎርም መልበስ ወይም መሣሪያ መታጠቅ ብቻ አይደለም ። ወታደርነት ማለት የሀገርን ክብር በነፍስ መጠበቅ የሕዝብን ተስፋ በደም ማቆየት የነፃነትን አደራ በትውልድ ላይ ማስቀጠል ነው።
ወታደር ማለት ሀገር ነው።
ሀገር ደግሞ በካርታ ላይ የተሳለ ድንበር ወይም ዝም ያለ መሬት አይደለችም።
ሀገር ማለት የአባቶች አደራ የእናቶች እንባ የጀግኖች መስዋዕትነት የሕፃናት ፈገግታ የወጣቶች ሕልም የአረጋውያን ተስፋ እና የመጪው ትውልድ እጣ ፈንታ ናት።
ሀገር ማለት
• የሕዝቧ ዘላቂ ሰላምና ደህንነት
• የሕፃናት ያልተቋረጠ የነፃነት ሳቅ
• የእናቶች የልብ እፎይታ
• የወጣቶች ብሩህ ተስፋ
• በነፃነት የሚተነፈስ አየርና በፍትሕ የሚገነባ ነገ ናት።
እነዚህን ሁሉ ክቡር እሴቶች በደሙና በሕይወቱ ዋጋ የሚጠብቀው ወታደር ነው። ለእያንዳንዱ የሰላም ሰከንድ የማይታይ መስዋዕትነት አለ ከእያንዳንዱ የነፃነት ቀን ጀርባም የብዙ ጀግኖች ደምና ታሪክ ተጽፎበታል።
ዛሬም ሀገሬ ኢትዮጵያ በጠራችኝ ጊዜ ሁሉ ከፊት የመቆም ግዴታዬን እየተወጣሁ እገኛለሁ። በብሔራዊ ምክክር ሂደት ውስጥ ስለ ሰላም ስለ አብሮነት ስለ ሀገራችን ቀጣይነት ስለ ፍትሕና ልማት ስለ ትውልድ የሚተርፍ አንድነት ከወገኖቼ ጋር በኃላፊነትና በቅንነት እየተመካከርኩ ነው።
ዛሬ ሁላችንም በታሪክ ፊት ቆመናል።
በዚህ ወሳኝ ወቅት የምንናገረው ቃል የምንወስነው ውሳኔ የምንፈፅመው ተግባር በዘመናት መዝገብ ላይ ይቀረፃል።
ስለዚህ ከልዩነታችን በላይ የሚያስተሳስረንን ሀገራችንን እናስቀድማለን ።
ከጊዜያዊ ክርክር በላይ ዘላቂ ሰላምን እንመርጣለን ከመከፋፈል ይልቅ መተባበርን እናከብራለን።
የሕዝብን ተስፋ ለማደናቀፍ የመግባባትን መንፈስ ለማዳከም የሚሞክሩ ድምፆች ሊኖሩ ይችላሉ
ነገር ግን እውነት ከአሉባልታ ይበልጣል አንድነት ከመከፋፈል ይበረታል የሕዝብ ፍቅር ከጥላቻ ይልቃል።
እኛ ኢትዮጵያውያን ነን።
የልዩነታችን ውበት አንድነታችንን አያጠፋም ይልቁን ያጎለብተዋል።
ሰላምን በጽናት ፍትሕን በብልህነት ሀገርን በፍቅር እንገነባለን።
ለኢትዮጵያ የሕይወት ቃልኪዳን
"ሀገሬ ኢትዮጵያ ሆይ!
ለአንቺ የማልከፍለው ዋጋ የማልሰጥሽ ጥረት የማልከብርሽ ክብር የለም።
በጠራሽኝ ጊዜ ሁሉ በየትኛውም ስፍራና በየትኛውም ዘመን ለነፃነትሽ ለሰላምሽ ለአንድነትሽ እና ለክብርሽ እቆማለሁ።
ይህ የፖለቲካ ቃል አይደለም ።
የሕይወቴ ቃልኪዳን ነው።
ይህ የዛሬ ውሳኔ ብቻ አይደለም ። ለመጪው ትውልድ የተቀመጠ አደራ ነው።
አሉባልታ ይጠፋል
ውሸት ይደበዝዛል
ጊዜ ያልፋል
ነገር ግን የታሪክ እውነት የሕዝብ ፍቅር የሀገር ክብር እና የጀግኖች መስዋዕትነት ለዘላለም ይኖራሉ ።
ታሪክ በቃላት አይገነባም በመስዋዕትነት ይጻፋል።
ሀገር በምኞት አትፀናም በአንድነት ትቆማለች።
ሕዝብ በፍርሃት አያድግም በተስፋ ያብባል።
ኢትዮጵያ በልጆቿ ፍቅር በልጆቿ ጥረት በልጆቿ አንድነት ለዘላለም ፀንታ ትኑር !
ለሐገሬና ለሕዝቤ የተገባ የሕይወት ቃልኪዳን ።
አለባቸው ደሳለኝ አበሻ (ኢትዮጵያ)
#ethiopia | እኔ ለኢትዮጵያ የተወለድሁ በኢትዮጵያ ያደግሁ ለኢትዮጵያም ሕይወቴን ለመስጠት በቃልኪዳን የቆምኩ ኩሩ ወታደር ነበርኩ ።
ወታደርነት ዩኒፎርም መልበስ ወይም መሣሪያ መታጠቅ ብቻ አይደለም ። ወታደርነት ማለት የሀገርን ክብር በነፍስ መጠበቅ የሕዝብን ተስፋ በደም ማቆየት የነፃነትን አደራ በትውልድ ላይ ማስቀጠል ነው።
ወታደር ማለት ሀገር ነው።
ሀገር ደግሞ በካርታ ላይ የተሳለ ድንበር ወይም ዝም ያለ መሬት አይደለችም።
ሀገር ማለት የአባቶች አደራ የእናቶች እንባ የጀግኖች መስዋዕትነት የሕፃናት ፈገግታ የወጣቶች ሕልም የአረጋውያን ተስፋ እና የመጪው ትውልድ እጣ ፈንታ ናት።
ሀገር ማለት
• የሕዝቧ ዘላቂ ሰላምና ደህንነት
• የሕፃናት ያልተቋረጠ የነፃነት ሳቅ
• የእናቶች የልብ እፎይታ
• የወጣቶች ብሩህ ተስፋ
• በነፃነት የሚተነፈስ አየርና በፍትሕ የሚገነባ ነገ ናት።
እነዚህን ሁሉ ክቡር እሴቶች በደሙና በሕይወቱ ዋጋ የሚጠብቀው ወታደር ነው። ለእያንዳንዱ የሰላም ሰከንድ የማይታይ መስዋዕትነት አለ ከእያንዳንዱ የነፃነት ቀን ጀርባም የብዙ ጀግኖች ደምና ታሪክ ተጽፎበታል።
ዛሬም ሀገሬ ኢትዮጵያ በጠራችኝ ጊዜ ሁሉ ከፊት የመቆም ግዴታዬን እየተወጣሁ እገኛለሁ። በብሔራዊ ምክክር ሂደት ውስጥ ስለ ሰላም ስለ አብሮነት ስለ ሀገራችን ቀጣይነት ስለ ፍትሕና ልማት ስለ ትውልድ የሚተርፍ አንድነት ከወገኖቼ ጋር በኃላፊነትና በቅንነት እየተመካከርኩ ነው።
ዛሬ ሁላችንም በታሪክ ፊት ቆመናል።
በዚህ ወሳኝ ወቅት የምንናገረው ቃል የምንወስነው ውሳኔ የምንፈፅመው ተግባር በዘመናት መዝገብ ላይ ይቀረፃል።
ስለዚህ ከልዩነታችን በላይ የሚያስተሳስረንን ሀገራችንን እናስቀድማለን ።
ከጊዜያዊ ክርክር በላይ ዘላቂ ሰላምን እንመርጣለን ከመከፋፈል ይልቅ መተባበርን እናከብራለን።
የሕዝብን ተስፋ ለማደናቀፍ የመግባባትን መንፈስ ለማዳከም የሚሞክሩ ድምፆች ሊኖሩ ይችላሉ
ነገር ግን እውነት ከአሉባልታ ይበልጣል አንድነት ከመከፋፈል ይበረታል የሕዝብ ፍቅር ከጥላቻ ይልቃል።
እኛ ኢትዮጵያውያን ነን።
የልዩነታችን ውበት አንድነታችንን አያጠፋም ይልቁን ያጎለብተዋል።
ሰላምን በጽናት ፍትሕን በብልህነት ሀገርን በፍቅር እንገነባለን።
ለኢትዮጵያ የሕይወት ቃልኪዳን
"ሀገሬ ኢትዮጵያ ሆይ!
ለአንቺ የማልከፍለው ዋጋ የማልሰጥሽ ጥረት የማልከብርሽ ክብር የለም።
በጠራሽኝ ጊዜ ሁሉ በየትኛውም ስፍራና በየትኛውም ዘመን ለነፃነትሽ ለሰላምሽ ለአንድነትሽ እና ለክብርሽ እቆማለሁ።
ይህ የፖለቲካ ቃል አይደለም ።
የሕይወቴ ቃልኪዳን ነው።
ይህ የዛሬ ውሳኔ ብቻ አይደለም ። ለመጪው ትውልድ የተቀመጠ አደራ ነው።
አሉባልታ ይጠፋል
ውሸት ይደበዝዛል
ጊዜ ያልፋል
ነገር ግን የታሪክ እውነት የሕዝብ ፍቅር የሀገር ክብር እና የጀግኖች መስዋዕትነት ለዘላለም ይኖራሉ ።
ታሪክ በቃላት አይገነባም በመስዋዕትነት ይጻፋል።
ሀገር በምኞት አትፀናም በአንድነት ትቆማለች።
ሕዝብ በፍርሃት አያድግም በተስፋ ያብባል።
ኢትዮጵያ በልጆቿ ፍቅር በልጆቿ ጥረት በልጆቿ አንድነት ለዘላለም ፀንታ ትኑር !
ለሐገሬና ለሕዝቤ የተገባ የሕይወት ቃልኪዳን ።
አለባቸው ደሳለኝ አበሻ (ኢትዮጵያ)
14 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የተባበሩት ዓረብ ኤሚሬቶች ለጎብኚዎች፣ ለንግድ ሰዎች እና ለቤተሰብ ጥሪ አገልግሎት የሚውል ለአምስት ዓመታት የሚያገለግል የብዙ ጊዜ መግቢያ (5-year multiple entry visa) ቪዛ በማቅረብ የዓለም አቀፍ የቱሪዝም እና የሥራ ማዕከልነቷን እያጠናከረች መሆኑን አስታወቀች። ይህ የቪዛ ዓይነት ማንኛውም የዓለም ዜጋ በየጊዜው አዲስ ቪዛ ማውጣት ሳያስፈልገው ለአምስት ዓመታት ያህል በተደጋጋሚ ወደ አገሪቱ እንዲገባና እንዲወጣ የሚያስችል ነው።
በአንድ ጊዜ መግቢያ ላይ ጎብኚዎች ለአምስት ዓመታት የቪዛ ዘመን ውስጥ በዓመት እስከ 90 ቀናት ድረስ መቆየት የሚችሉ ሲሆን፣ አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ ደግሞ ይህን የቆይታ ጊዜ ለተጨማሪ 90 ቀናት በማራዘም በአጠቃላይ በአንድ ዓመት ውስጥ እስከ 180 ቀናት እንዲቆዩ ይፈቅዳል። ይህ አሰራር በዓመቱ ውስጥ ጥቅም ላይ ያልዋሉ ቀናትን ወደሚቀጥለው ዓመት ለማዘዋወር አይፈቅድም።
የቪዛው አመልካቾች ማሟላት ከሚገባቸው ዋና ዋና መስፈርቶች መካከል ቢያንስ ለስድስት ወራት የሚያገለግል ፓስፖርት፣ የተረጋገጠ የጉዞ ትኬት፣ ሕጋዊ የጤና ኢንሹራንስ፣ እና ማመልከቻው ከመግባቱ በፊት ባለፉት ስድስት ወራት ውስጥ 4 ሺህ የአሜሪካ ዶላር ወይም ተመሳሳይ መጠን ያለው የባንክ ሂሳብ እንቅስቃሴ ማሳየት ይጠበቅባቸዋል። በተጨማሪም ከ18 ዓመት በታች ለሆኑ ሕፃናት የቤተሰብ ማመልከቻ ማቅረብ የሚቻል ሲሆን፣ የአንዳንድ አገራት ዜጎች ደግሞ የመታወቂያ ኮፒ ማያያዝ ይጠበቅባቸዋል።
አመልካቾች በይነመረብን በመጠቀም በስማርት አገልግሎቶች ወይም በአካል ወደ ደንበኞች ማዕከል በመሄድ ማመልከት የሚችሉ ሲሆን፣ የቪዛ ሂደቱም በ48 ሰዓታት ውስጥ ይጠናቀቃል። የቪዛው ክፍያ እንደ ማመልከቻው ቦታ የሚለያይ ሲሆን፣ የዋስትና ገንዘብን (ዲፖዚት) ጨምሮ ከ3,700 በላይ ዲርሃም ወጪ ይደረግበታል። ማመልከቻው ውድቅ ከተደረገ ወይም ከተሰረዘ የተቀመጠው የዋስትና ገንዘብ እና የኢንሹራንስ ክፍያ ተመላሽ የሚደረግ ሲሆን፣ የቆይታ ጊዜ ሕግ ከተጣሰ ግን የተቀመጠው የዋስትና ገንዘብ ለመንግሥት ገቢ ይሆናል።
በአንድ ጊዜ መግቢያ ላይ ጎብኚዎች ለአምስት ዓመታት የቪዛ ዘመን ውስጥ በዓመት እስከ 90 ቀናት ድረስ መቆየት የሚችሉ ሲሆን፣ አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ ደግሞ ይህን የቆይታ ጊዜ ለተጨማሪ 90 ቀናት በማራዘም በአጠቃላይ በአንድ ዓመት ውስጥ እስከ 180 ቀናት እንዲቆዩ ይፈቅዳል። ይህ አሰራር በዓመቱ ውስጥ ጥቅም ላይ ያልዋሉ ቀናትን ወደሚቀጥለው ዓመት ለማዘዋወር አይፈቅድም።
የቪዛው አመልካቾች ማሟላት ከሚገባቸው ዋና ዋና መስፈርቶች መካከል ቢያንስ ለስድስት ወራት የሚያገለግል ፓስፖርት፣ የተረጋገጠ የጉዞ ትኬት፣ ሕጋዊ የጤና ኢንሹራንስ፣ እና ማመልከቻው ከመግባቱ በፊት ባለፉት ስድስት ወራት ውስጥ 4 ሺህ የአሜሪካ ዶላር ወይም ተመሳሳይ መጠን ያለው የባንክ ሂሳብ እንቅስቃሴ ማሳየት ይጠበቅባቸዋል። በተጨማሪም ከ18 ዓመት በታች ለሆኑ ሕፃናት የቤተሰብ ማመልከቻ ማቅረብ የሚቻል ሲሆን፣ የአንዳንድ አገራት ዜጎች ደግሞ የመታወቂያ ኮፒ ማያያዝ ይጠበቅባቸዋል።
አመልካቾች በይነመረብን በመጠቀም በስማርት አገልግሎቶች ወይም በአካል ወደ ደንበኞች ማዕከል በመሄድ ማመልከት የሚችሉ ሲሆን፣ የቪዛ ሂደቱም በ48 ሰዓታት ውስጥ ይጠናቀቃል። የቪዛው ክፍያ እንደ ማመልከቻው ቦታ የሚለያይ ሲሆን፣ የዋስትና ገንዘብን (ዲፖዚት) ጨምሮ ከ3,700 በላይ ዲርሃም ወጪ ይደረግበታል። ማመልከቻው ውድቅ ከተደረገ ወይም ከተሰረዘ የተቀመጠው የዋስትና ገንዘብ እና የኢንሹራንስ ክፍያ ተመላሽ የሚደረግ ሲሆን፣ የቆይታ ጊዜ ሕግ ከተጣሰ ግን የተቀመጠው የዋስትና ገንዘብ ለመንግሥት ገቢ ይሆናል።
Sponsored by
Surafel
15 days ago
በሀገር ፍቅር ቲያትር ቤት የሦስት መጽሐፍት የምረቃ ሥነ ሥርዓት
#ethiopia | መምህር ገላውዴዎስ አለልኝ ያዘጋጃቸው ሦስት አዳዲስ ትምህርታዊ መጽሐፍት ቅዳሜ ሀምሌ 25 ቀን 2018 ዓ.ም. (08:00 ሰዓት) ጀምሮ በፒያሳ በሚገኘው በሀገር ፍቅር ቲያትር ቤት በይፋ ይመረቃሉ።
የሚመረቁት መጽሐፍት፦
የጎበዝ ልጆች ቤተ መጻሕፍት
የምጡቅ አዕምሮ ልጆች ፈተና
የልጆች የእውቀት ገበታ
እነዚህ መጽሐፍት ሕፃናት የማሰብ ችሎታቸውን፣ አጠቃላይ ዕውቀታቸውን እና የመማር ፍላጎታቸውን እንዲያጎለብቱ በጥንቃቄ የተዘጋጁ ሲሆን፣ ከሀገር ውስጥና ከውጭ ያሉ ታላላቅ ሰዎችን፣ ጠቅላላ ዕውቀቶችን እና አነቃቂ ትምህርቶችን በቀላል አቀራረብ ያቀርባሉ።
የጎበዝ ልጆች ቤተ መጻሕፍት 30 ምዕራፎችን የያዘ ሲሆን፣ ለሕፃናት እና ለአዋቂዎች ጭምር ጠቃሚ የሆኑ አጠቃላይ ዕውቀቶችን ያካተተ ትምህርታዊ መጽሐፍ ነው።
የምጡቅ አዕምሮ ልጆች ፈተና በ25 ምዕራፎች የተዋቀረ ሲሆን፣ የሕፃናትን ዕውቀት፣ የማሰብ ችሎታ እና የመማር ፍላጎት ለማሳደግ የተዘጋጀ ነው።
የልጆች የእውቀት ገበታ 27 ምዕራፎችን የያዘ ይህ መጽሐፍ ልጆች አጠቃላይ ዕውቀታቸውን እንዲያሳድጉ፣ የማሰብ ችሎታቸውን እንዲያጠናክሩ እና ለትምህርታቸው ጠንካራ መሠረት እንዲጥሉ በቀላል እና ግልጽ አቀራረብ ተዘጋጅቷል።
ሁላችሁም በዚህ የመጽሐፍ ምረቃ ሥነ ሥርዓት ላይ በመገኘት ደራሲውን እንዲያበረታቱ በአክብሮት ተጋብዛችኋል።
#ethiopia | መምህር ገላውዴዎስ አለልኝ ያዘጋጃቸው ሦስት አዳዲስ ትምህርታዊ መጽሐፍት ቅዳሜ ሀምሌ 25 ቀን 2018 ዓ.ም. (08:00 ሰዓት) ጀምሮ በፒያሳ በሚገኘው በሀገር ፍቅር ቲያትር ቤት በይፋ ይመረቃሉ።
የሚመረቁት መጽሐፍት፦
የጎበዝ ልጆች ቤተ መጻሕፍት
የምጡቅ አዕምሮ ልጆች ፈተና
የልጆች የእውቀት ገበታ
እነዚህ መጽሐፍት ሕፃናት የማሰብ ችሎታቸውን፣ አጠቃላይ ዕውቀታቸውን እና የመማር ፍላጎታቸውን እንዲያጎለብቱ በጥንቃቄ የተዘጋጁ ሲሆን፣ ከሀገር ውስጥና ከውጭ ያሉ ታላላቅ ሰዎችን፣ ጠቅላላ ዕውቀቶችን እና አነቃቂ ትምህርቶችን በቀላል አቀራረብ ያቀርባሉ።
የጎበዝ ልጆች ቤተ መጻሕፍት 30 ምዕራፎችን የያዘ ሲሆን፣ ለሕፃናት እና ለአዋቂዎች ጭምር ጠቃሚ የሆኑ አጠቃላይ ዕውቀቶችን ያካተተ ትምህርታዊ መጽሐፍ ነው።
የምጡቅ አዕምሮ ልጆች ፈተና በ25 ምዕራፎች የተዋቀረ ሲሆን፣ የሕፃናትን ዕውቀት፣ የማሰብ ችሎታ እና የመማር ፍላጎት ለማሳደግ የተዘጋጀ ነው።
የልጆች የእውቀት ገበታ 27 ምዕራፎችን የያዘ ይህ መጽሐፍ ልጆች አጠቃላይ ዕውቀታቸውን እንዲያሳድጉ፣ የማሰብ ችሎታቸውን እንዲያጠናክሩ እና ለትምህርታቸው ጠንካራ መሠረት እንዲጥሉ በቀላል እና ግልጽ አቀራረብ ተዘጋጅቷል።
ሁላችሁም በዚህ የመጽሐፍ ምረቃ ሥነ ሥርዓት ላይ በመገኘት ደራሲውን እንዲያበረታቱ በአክብሮት ተጋብዛችኋል።
21 days ago
የአሜሪካ ጥቃት ሰባት ሰዎችን መግደሉን ኢራን ገለጸች
አሜሪካ ለስድስተኛ ተከታታይ ምሽት በኢራን ላይ ጥቃት ማድረሷን ተከትሎ ቴህራን በርካታ ሰዎች መሞታቸውን የዘገበች ሲሆን፥ ጥቃቱ የሀገሪቱ ደቡባዊ ክፍል የመሠረተ ልማት አውታሮች ላይ ያነጣጠረ ነበር ተብሏል።
የአሜሪካ ማዕከላዊ እዝ ጥቃቱ «የኢራንን ወታደራዊ አቅም ለማዳከም» የተደረገ ጥረት ነዉ ብሏል፡፡
እነዚህ ጥቃቶች ሁለቱ ሀገራት ባለፈው ወር የተፈራረሙት ጊዜያዊ ስምምነት አደጋ ላይ መውደቁን ያሳያሉ።
የአሜሪካ ወታደራዊ ክፍል በኦማን ባሕረ ሰላጤ ላይ የእገዳ ጥሰት የሞከሩ ሶስት የንግድ መርከቦችን አቅጣጫ ማስቀየሩን እና አንዷን መርከብ ከጥቅም ውጭ ማድረጉን አስታውቋል።
በሌላ በኩል እንደ ኳታር፣ ዮርዳኖስ እና ባህሬን ያሉ የባሕረ ሰላጤው ሀገራት የመሠረተ ልማት ጥበቃቸውን እና ወታደራዊ ዝግጁነታቸውን እያጠናከሩ ነው።
የኢራን እስላማዊ አብዮታዊ ጥበቃ ጦር በአህቫዝ ከተማ ለሚገኝ የሕፃናት ካንሰር ሆስፒታል መፈናቀል ምላሽ ለመስጠት በባህሬን በሚገኝ የአሜሪካ አየር ኃይል ጣቢያ ላይ ጥቃት መፈጸሙን አስታውቋል።
የኢራን ጦር ቃል አቀባይ ብርጋዴር ጄኔራል መሐመድ አክራሚኒያ የአሜሪካ ጥቃቶች ከቀጠሉ የኢራን እርምጃ «ወደ አዳዲስ አካባቢዎች እንደሚስፋፋ» አስጠንቅቀዋል።
አሜሪካ ኢራን ወደ ድርድሩ እንድትመለስ ስትፈልግ፥ ኢራን ደግሞ አሜሪካ መጀመሪያ እገዳውን እንድታነሳ ትፈልጋለች።
የዋይት ሀውስ ፕሬስ ሴክሬተሪ ካሮሊን ሌቪት፤ ትራምፕ ኢራንን ተጠያቂ እንደሚያደርጉ ነገር ግን ሁልጊዜ ለዲፕሎማሲ ክፍት መሆናቸውን ገልጸው፥ መርከቦች ላይ የሚሰነዘር ጥቃትን ግን እንደማይፈቅዱ ተናግረዋል።
የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ግን በአሁኑ ወቅት ከዋሽንግተን ጋር ለመነጋገር ምንም ዓይነት እቅድ እንደሌለውና ትኩረቱ ሀገሪቱን መከላከል ላይ ብቻ መሆኑን አስታውቋል።
ሳራ ዮሐንስ
አሜሪካ ለስድስተኛ ተከታታይ ምሽት በኢራን ላይ ጥቃት ማድረሷን ተከትሎ ቴህራን በርካታ ሰዎች መሞታቸውን የዘገበች ሲሆን፥ ጥቃቱ የሀገሪቱ ደቡባዊ ክፍል የመሠረተ ልማት አውታሮች ላይ ያነጣጠረ ነበር ተብሏል።
የአሜሪካ ማዕከላዊ እዝ ጥቃቱ «የኢራንን ወታደራዊ አቅም ለማዳከም» የተደረገ ጥረት ነዉ ብሏል፡፡
እነዚህ ጥቃቶች ሁለቱ ሀገራት ባለፈው ወር የተፈራረሙት ጊዜያዊ ስምምነት አደጋ ላይ መውደቁን ያሳያሉ።
የአሜሪካ ወታደራዊ ክፍል በኦማን ባሕረ ሰላጤ ላይ የእገዳ ጥሰት የሞከሩ ሶስት የንግድ መርከቦችን አቅጣጫ ማስቀየሩን እና አንዷን መርከብ ከጥቅም ውጭ ማድረጉን አስታውቋል።
በሌላ በኩል እንደ ኳታር፣ ዮርዳኖስ እና ባህሬን ያሉ የባሕረ ሰላጤው ሀገራት የመሠረተ ልማት ጥበቃቸውን እና ወታደራዊ ዝግጁነታቸውን እያጠናከሩ ነው።
የኢራን እስላማዊ አብዮታዊ ጥበቃ ጦር በአህቫዝ ከተማ ለሚገኝ የሕፃናት ካንሰር ሆስፒታል መፈናቀል ምላሽ ለመስጠት በባህሬን በሚገኝ የአሜሪካ አየር ኃይል ጣቢያ ላይ ጥቃት መፈጸሙን አስታውቋል።
የኢራን ጦር ቃል አቀባይ ብርጋዴር ጄኔራል መሐመድ አክራሚኒያ የአሜሪካ ጥቃቶች ከቀጠሉ የኢራን እርምጃ «ወደ አዳዲስ አካባቢዎች እንደሚስፋፋ» አስጠንቅቀዋል።
አሜሪካ ኢራን ወደ ድርድሩ እንድትመለስ ስትፈልግ፥ ኢራን ደግሞ አሜሪካ መጀመሪያ እገዳውን እንድታነሳ ትፈልጋለች።
የዋይት ሀውስ ፕሬስ ሴክሬተሪ ካሮሊን ሌቪት፤ ትራምፕ ኢራንን ተጠያቂ እንደሚያደርጉ ነገር ግን ሁልጊዜ ለዲፕሎማሲ ክፍት መሆናቸውን ገልጸው፥ መርከቦች ላይ የሚሰነዘር ጥቃትን ግን እንደማይፈቅዱ ተናግረዋል።
የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ግን በአሁኑ ወቅት ከዋሽንግተን ጋር ለመነጋገር ምንም ዓይነት እቅድ እንደሌለውና ትኩረቱ ሀገሪቱን መከላከል ላይ ብቻ መሆኑን አስታውቋል።
ሳራ ዮሐንስ
21 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) በትግራይ ክልል የጦርነት ስጋት ዳግም በማንዣበቡ የክልሉ ባለሥልጣናት የቀድሞ የትግራይ መከላከያ ኃይል (ትመኃ/TDF) ታጋዮች በድጋሚ እንዲመዘገቡ ጥሪ እያቀረቡ ባሉበት በአሁኑ ወቅት፣ በ2013-2015 ዓ.ም (የፈረንጆቹ 2020-2022) የነበረውን የእርስ በርስ ጦርነት የተቀላቀሉ ሴት ታጋዮች በራሳቸው ወታደራዊ አዛዦች ይፈጸምባቸው የነበረውን የፆታዊ እና የጉልበት ብዝበዛ በይፋ ማጋለጥ ጀምረዋል።
በጦርነቱ ወቅት የተፈጸሙ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶችን በተመለከተ የሚወጡ ሪፖርቶች በብዛት ትኩረት የሚያደርጉት በፌደራሉ መንግሥት፣ በኤርትራ እና በአማራ ኃይሎች ተፈጽመዋል በተባሉ በደሎች ላይ ቢሆንም፤ ለትግራይ ሴቶች ፍትሕ መረጋገጥ ግን በትግራይ መከላከያ ኃይል አዛዦች በሴት ታጋዮች ላይ የተፈጸሙ የወሲብ ጥቃቶችንም በትኩረት መመልከትን እንደሚጠይቅ ዘ ኒው ሂውማኒቴሪያን የተሰኘው የዜና ድርጅት ያጠናቀረው ዘገባ ያመላክታል። የዜና ድርጅቱ ከሁለት ደርዘን በላይ የሚሆኑ የቀድሞ ሴትና ወንድ ታጋዮችን በማነጋገር የጥቃቱን ስፋት እና በወቅቱ ከፍተኛ ወታደራዊ አመራሩ "የጦርነቱን አካሄድ ያዳክማል" በሚል ስጋት ጉዳዩን እንዴት ችላ እንዳለው መርምሯል።
የሥልጣን አለግባብ አጠቃቀም እና "አስገዳጅ ሁኔታዎች"
በዘገባው ላይ ስማቸው የተቀየረው እንደ ቲርሃስ ያሉ ታጋዮች እንደሚገልጹት፣ ብዙ ሴቶች ጦርነቱን የተቀላቀሉት ከጠላት ኃይሎች ጥቃት ጥገኝነትን ፍለጋ ቢሆንም፣ በገዛ ክፍለ ጦራቸው ውስጥ ግን ለከፋ አደጋ ተጋልጠዋል። ቲርሃስ በምርመራ ቡድን ውስጥ በመሳተፍ ባሰባሰበችው መረጃ መሠረት፣ አንድ ወታደራዊ ኮሎኔል ሴቶችን ለሥልጠና ከማዘጋጀት ይልቅ መድኃኒት እያጠጣ ይደፍራቸው የነበረ ሲሆን፣ ከተጎጂዎቹ መካከል ዕድሜያቸው እስከ 12 ዓመት የሆኑ ሕፃናት ይገኙበት ነበር። ይህንን የኮሎኔሉን ድርጊት የተቃወሙ ሴቶች ደግሞ ሕክምና ሳይጨርሱ ወደ ግንባር እንዲመለሱ መደረግን ጨምሮ የተለያዩ የማስፈራሪያና የእንግልት እርምጃዎች ይወሰዱባቸው ነበር።
ሌላው አዌት የተባለ ወንድ ታጋይ እንደገለጸው፣ ከፍተኛ መኮንኖች ወጣት ሴት ታጋዮችን ለወሲባዊ ጥቅም ሲሉ ይበልጥ ምቹ የሆኑ የ"ራዲዮ ኦፕሬተር" እና የ"ጸሐፊነት" የሥራ መደቦች ላይ ይመድቧቸው ነበር፤ ይህም በወቅቱ በሰፊው የተለመደ ተግባር ነበር። ፈቃደኛ ያልሆኑት ደግሞ አስቸጋሪ በሆኑ የግንባር ስምሪቶች ይቀጡ ነበር።
በትግራይ መከላከያ ኃይል ውስጥ የሴቶችን አቤቱታዎች የሚያዳምጥ የሴቶች ጉዳይ ተወካይ የክትትል ሥርዓት በ2013 ዓ.ም ተዘርግቶ የነበረ ቢሆንም፣ በተግባር ግን አሠራሩ ደካማና አመራሩን ጥፋተኛ ከማድረግ ይልቅ የወቀሳ ሰለባ የሚያደርግ ነበር።
ሳዕሬ የተባሉ የቀድሞ የሕወሃት ከፍተኛ አመራር የነበረውን ሁኔታ "የመከላከያ ስንፍና" ሲሉ ይጠሩታል። እንደ እሳቸው ገለጻ፣ በጦርነቱ ወቅት ወታደራዊ አመራሩ "የውስጥ አንድነትን ማሳየት" ላይ ብቻ ያተኮረ በመሆኑ የሴቶች ደኅንነት ጉዳይ ወደ ጎን ተገፍቶ ቆይቷል። ራህዋ የተባለች ከፍተኛ የትግራይ መከላከያ ኃይል ሴት አባልም ይህንን ድክመት አምናለች፤ "የጠላትን ወንጀል የሚያሳንስ እንዳይመስል በሚል ስጋት ለጉዳዩ በቂ ትኩረት አልሰጠንም ነበር" ስትል ተናግራለች። ሎዛን የተባለች የቀድሞ ታጋይም ብዙ ሴቶች የራሳቸውን ደኅንነት ከመጠበቅ ይልቅ ጦርነቱን ማሸነፍ ላይ ብቻ ትኩረት በማድረጋቸው ዝምታን መምረጣቸውን ገልጻለች።
በ2015 ዓ.ም የፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት ከተፈረመ በኋላም ቢሆን ለሴቶች ያለው ሁኔታ ይበልጥ አስቸጋሪ ሆኗል። የሰላም ስምምነቱ ሙሉ በሙሉ ባለመተግበሩ ወደ አንድ ሚሊዮን የሚጠጉ የትግራይ ተፈናቃዮች (አብዛኞቹ ሴቶች) አሁንም ወደ ቀያቸው አልተመለሱም።
በአሁኑ ወቅት በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ውስጥ ያለው የፖለቲካ መከፋፈል፣ ሥራ አጥነት፣ እና የኑሮ ውድነት እያደገ መምጣት፣ በጦርነቱ ወቅት የተፈጸሙ የፆታ ጥቃቶችን እና የፍትሕ ጉዳዮችን አጀንዳ አድርጎ ለመነጋገር ምቹ ሁኔታን አልፈጠረም። ይሁን እንጂ በትግራይ ክልል እውነተኛ ፍትሕና ተጠያቂነት እንዲሰፍን ከተፈለገ፣ ሴቶች በገዛ ጓዶቻቸው እጅ የደረሰባቸውን በደል ጭምር በአግባቡ መመርመርና መፍትሔ መስጠት እንደሚገባ የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች ያሳስባሉ።
በጦርነቱ ወቅት የተፈጸሙ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶችን በተመለከተ የሚወጡ ሪፖርቶች በብዛት ትኩረት የሚያደርጉት በፌደራሉ መንግሥት፣ በኤርትራ እና በአማራ ኃይሎች ተፈጽመዋል በተባሉ በደሎች ላይ ቢሆንም፤ ለትግራይ ሴቶች ፍትሕ መረጋገጥ ግን በትግራይ መከላከያ ኃይል አዛዦች በሴት ታጋዮች ላይ የተፈጸሙ የወሲብ ጥቃቶችንም በትኩረት መመልከትን እንደሚጠይቅ ዘ ኒው ሂውማኒቴሪያን የተሰኘው የዜና ድርጅት ያጠናቀረው ዘገባ ያመላክታል። የዜና ድርጅቱ ከሁለት ደርዘን በላይ የሚሆኑ የቀድሞ ሴትና ወንድ ታጋዮችን በማነጋገር የጥቃቱን ስፋት እና በወቅቱ ከፍተኛ ወታደራዊ አመራሩ "የጦርነቱን አካሄድ ያዳክማል" በሚል ስጋት ጉዳዩን እንዴት ችላ እንዳለው መርምሯል።
የሥልጣን አለግባብ አጠቃቀም እና "አስገዳጅ ሁኔታዎች"
በዘገባው ላይ ስማቸው የተቀየረው እንደ ቲርሃስ ያሉ ታጋዮች እንደሚገልጹት፣ ብዙ ሴቶች ጦርነቱን የተቀላቀሉት ከጠላት ኃይሎች ጥቃት ጥገኝነትን ፍለጋ ቢሆንም፣ በገዛ ክፍለ ጦራቸው ውስጥ ግን ለከፋ አደጋ ተጋልጠዋል። ቲርሃስ በምርመራ ቡድን ውስጥ በመሳተፍ ባሰባሰበችው መረጃ መሠረት፣ አንድ ወታደራዊ ኮሎኔል ሴቶችን ለሥልጠና ከማዘጋጀት ይልቅ መድኃኒት እያጠጣ ይደፍራቸው የነበረ ሲሆን፣ ከተጎጂዎቹ መካከል ዕድሜያቸው እስከ 12 ዓመት የሆኑ ሕፃናት ይገኙበት ነበር። ይህንን የኮሎኔሉን ድርጊት የተቃወሙ ሴቶች ደግሞ ሕክምና ሳይጨርሱ ወደ ግንባር እንዲመለሱ መደረግን ጨምሮ የተለያዩ የማስፈራሪያና የእንግልት እርምጃዎች ይወሰዱባቸው ነበር።
ሌላው አዌት የተባለ ወንድ ታጋይ እንደገለጸው፣ ከፍተኛ መኮንኖች ወጣት ሴት ታጋዮችን ለወሲባዊ ጥቅም ሲሉ ይበልጥ ምቹ የሆኑ የ"ራዲዮ ኦፕሬተር" እና የ"ጸሐፊነት" የሥራ መደቦች ላይ ይመድቧቸው ነበር፤ ይህም በወቅቱ በሰፊው የተለመደ ተግባር ነበር። ፈቃደኛ ያልሆኑት ደግሞ አስቸጋሪ በሆኑ የግንባር ስምሪቶች ይቀጡ ነበር።
በትግራይ መከላከያ ኃይል ውስጥ የሴቶችን አቤቱታዎች የሚያዳምጥ የሴቶች ጉዳይ ተወካይ የክትትል ሥርዓት በ2013 ዓ.ም ተዘርግቶ የነበረ ቢሆንም፣ በተግባር ግን አሠራሩ ደካማና አመራሩን ጥፋተኛ ከማድረግ ይልቅ የወቀሳ ሰለባ የሚያደርግ ነበር።
ሳዕሬ የተባሉ የቀድሞ የሕወሃት ከፍተኛ አመራር የነበረውን ሁኔታ "የመከላከያ ስንፍና" ሲሉ ይጠሩታል። እንደ እሳቸው ገለጻ፣ በጦርነቱ ወቅት ወታደራዊ አመራሩ "የውስጥ አንድነትን ማሳየት" ላይ ብቻ ያተኮረ በመሆኑ የሴቶች ደኅንነት ጉዳይ ወደ ጎን ተገፍቶ ቆይቷል። ራህዋ የተባለች ከፍተኛ የትግራይ መከላከያ ኃይል ሴት አባልም ይህንን ድክመት አምናለች፤ "የጠላትን ወንጀል የሚያሳንስ እንዳይመስል በሚል ስጋት ለጉዳዩ በቂ ትኩረት አልሰጠንም ነበር" ስትል ተናግራለች። ሎዛን የተባለች የቀድሞ ታጋይም ብዙ ሴቶች የራሳቸውን ደኅንነት ከመጠበቅ ይልቅ ጦርነቱን ማሸነፍ ላይ ብቻ ትኩረት በማድረጋቸው ዝምታን መምረጣቸውን ገልጻለች።
በ2015 ዓ.ም የፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት ከተፈረመ በኋላም ቢሆን ለሴቶች ያለው ሁኔታ ይበልጥ አስቸጋሪ ሆኗል። የሰላም ስምምነቱ ሙሉ በሙሉ ባለመተግበሩ ወደ አንድ ሚሊዮን የሚጠጉ የትግራይ ተፈናቃዮች (አብዛኞቹ ሴቶች) አሁንም ወደ ቀያቸው አልተመለሱም።
በአሁኑ ወቅት በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ውስጥ ያለው የፖለቲካ መከፋፈል፣ ሥራ አጥነት፣ እና የኑሮ ውድነት እያደገ መምጣት፣ በጦርነቱ ወቅት የተፈጸሙ የፆታ ጥቃቶችን እና የፍትሕ ጉዳዮችን አጀንዳ አድርጎ ለመነጋገር ምቹ ሁኔታን አልፈጠረም። ይሁን እንጂ በትግራይ ክልል እውነተኛ ፍትሕና ተጠያቂነት እንዲሰፍን ከተፈለገ፣ ሴቶች በገዛ ጓዶቻቸው እጅ የደረሰባቸውን በደል ጭምር በአግባቡ መመርመርና መፍትሔ መስጠት እንደሚገባ የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች ያሳስባሉ።
21 days ago
በሀገራዊ ምክክር መድረክ ላይ የተገላገለችው እናት ልጇን "ምክክር" ስትል ሰየመችው::
የሀገር ፍቅር እና የቁርጠኝነት ትልቅ ማሳያ የሆነችው ወጣት ክርኑዶ ኡጁሉ፣ የመውለጃዋ ቀን ተቃርቦ ሳለ “ሀገሬ ጠርታኝ አልቀርም” በሚል ትልቅ አላማ ከጋምቤላ ክልል ወደ አዲስ አበባ በመምጣት በሀገራዊ ምክክር ጉባኤው ላይ ስትሳተፍ ቆይታለች።
በጉባኤው ሂደት ላይ እያለችም በዘውዲቱ ሆስፒታል ወንድ ልጅ በሰላም ተገላግላለች።
ይህንን ተከትሎም የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ እና የጋምቤላ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ወ/ሮ አለሚቱ ኡመድ እናቲቱ ባረፈችበት ቤት በአካል በመገኘት እንኳን ደስ አለሽ ብለዋታል።
ወጣቷ እናት የተለመደውን የቤተሰብ ስም የማውጣት ባህል በመተው፣ የልጇን ስም የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽኑ እንዲያወጣላት በጠየቀችው መሠረት የሕፃኑ ስም "ምክክር" ተብሎ ተሰይሟል።
ከጥቂት ቀናት እረፍት በኋላ የመጣችበትን ታላቅ ሀገራዊ ዓላማ ለማሳካት ወደ ምክክር ጉባኤው በልበ ሙሉነት እንደምትመለስ ያረጋገጠች ሲሆን፣ ጉባኤውን አጠናቃ ወደ መጣችበት እስክትመለስ ድረስ ለእሷና ለልጇ የሚያስፈልገው ሁሉን አቀፍ ድጋፍ እንደሚደረግላት ተገልጿል።
ከንቲባ አዳነች አቤቤ ባስተላለፉት መልዕክት፣ ይህ ታሪክ ለሀገሪቱ ወቅታዊ ሁኔታ ትልቅ ማሳያ መሆኑን ጠቅሰው፣ እናቲቱ በሰላም ተገላግላ በደስታ እንደተሞላች ሁሉ ሀገሪቱም ከገጠሟት ፈተናዎች በምክክር እና በውይይት ተገላግላ ወደ ተሻለ የሽግግር ምዕራፍ እንደምትሻገር ፅኑ እምነታቸውን ገልጸው ለሕፃኑ እና ለኢትዮጵያ ሕፃናት በሙሉ መልካም ምኞታቸውን አስተላልፈዋል።
Seledadotio
Seledadotio
የሀገር ፍቅር እና የቁርጠኝነት ትልቅ ማሳያ የሆነችው ወጣት ክርኑዶ ኡጁሉ፣ የመውለጃዋ ቀን ተቃርቦ ሳለ “ሀገሬ ጠርታኝ አልቀርም” በሚል ትልቅ አላማ ከጋምቤላ ክልል ወደ አዲስ አበባ በመምጣት በሀገራዊ ምክክር ጉባኤው ላይ ስትሳተፍ ቆይታለች።
በጉባኤው ሂደት ላይ እያለችም በዘውዲቱ ሆስፒታል ወንድ ልጅ በሰላም ተገላግላለች።
ይህንን ተከትሎም የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ እና የጋምቤላ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ወ/ሮ አለሚቱ ኡመድ እናቲቱ ባረፈችበት ቤት በአካል በመገኘት እንኳን ደስ አለሽ ብለዋታል።
ወጣቷ እናት የተለመደውን የቤተሰብ ስም የማውጣት ባህል በመተው፣ የልጇን ስም የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽኑ እንዲያወጣላት በጠየቀችው መሠረት የሕፃኑ ስም "ምክክር" ተብሎ ተሰይሟል።
ከጥቂት ቀናት እረፍት በኋላ የመጣችበትን ታላቅ ሀገራዊ ዓላማ ለማሳካት ወደ ምክክር ጉባኤው በልበ ሙሉነት እንደምትመለስ ያረጋገጠች ሲሆን፣ ጉባኤውን አጠናቃ ወደ መጣችበት እስክትመለስ ድረስ ለእሷና ለልጇ የሚያስፈልገው ሁሉን አቀፍ ድጋፍ እንደሚደረግላት ተገልጿል።
ከንቲባ አዳነች አቤቤ ባስተላለፉት መልዕክት፣ ይህ ታሪክ ለሀገሪቱ ወቅታዊ ሁኔታ ትልቅ ማሳያ መሆኑን ጠቅሰው፣ እናቲቱ በሰላም ተገላግላ በደስታ እንደተሞላች ሁሉ ሀገሪቱም ከገጠሟት ፈተናዎች በምክክር እና በውይይት ተገላግላ ወደ ተሻለ የሽግግር ምዕራፍ እንደምትሻገር ፅኑ እምነታቸውን ገልጸው ለሕፃኑ እና ለኢትዮጵያ ሕፃናት በሙሉ መልካም ምኞታቸውን አስተላልፈዋል።
Seledadotio
Seledadotio
21 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) በዚህ ሳምንት በካናዳ እና በሚኒሶታ ከተከሰቱ ግዙፍ የሰደድ እሳቶች የሚወጣው ከባድ ጢስ፣ በመካከለኛው ምዕራብ እና በሰሜን ምሥራቅ አሜሪካ የሚገኙ ሰፊ አካባቢዎችን ያዳረሰ ሲሆን፣ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎችን ለከፍተኛ እና አደገኛ የአየር ብክለት አጋልጧል። በካናዳ ከ100 በላይ የሰደድ እሳቶች ከቁጥጥር ውጭ ሆነው እየነደዱ የሚገኙ ሲሆን፣ ኃይለኛ ነፋስ ጢሱን ወደ ደቡብ ምሥራቅ አቅጣጫ እየገፋው ይገኛል። በተጨማሪም በሰሜናዊ ሚኒሶታ በርካታ የሰደድ እሳቶች ተከስተዋል።
ከእሳቱ የሚወጣው ከፍተኛ መጠን ያለው ጥቃቅን ብናኝ በተለይም ለሕፃናት፣ እንዲሁም የልብ እና የሳምባ ሕመም ላለባቸው የኅብረተሰብ ክፍሎች እጅግ አደገኛ መሆኑ ተነግሯል። ባለፈው ሐሙስ ዕለት ሚኒያፖሊስ፣ ቺካጎ እና ዲትሮይት በዓለም ላይ ከፍተኛ የአየር ብክለት ካለባቸው አምስት ዋና ዋና ከተሞች ዝርዝር ውስጥ ገብተዋል። የአየር ጥራት ማስጠንቀቂያው ከሚኒሶታ አንስቶ እስከ ሰሜን ምሥራቅ አሜሪካ የተዘረጋ ሲሆን፣ የሚኒሶታ ባለሥልጣናት የትዊን ሲቲስ የሜትሮ አካባቢን ጨምሮ እስከ አርብ የሚቆይ የአየር ጥራት ማስጠንቀቂያ አውጥተዋል። በተለይም በሰሜን ምሥራቅ ሚኒሶታ የአየር ጥራቱ ለማንም ሰው ደኅንነቱ የተጠበቀ ወደማይሆንበት አደገኛ ደረጃ ደርሷል።
በመላው የኒው ዮርክ ግዛት ማሳሰቢያ የወጣ ሲሆን፣ ለተጓዦች የፊት ጭንብል እንደሚከፋፈል ባለሥልጣናት ገልጸዋል። ፔንሲልቬንያ በበኩሏ እጅግ አደገኛ የሆነውን የቀይ ኮድ የአየር ጥራት ማስጠንቀቂያ አስተላልፋለች። በሚቺጋን እና ማሳቹሴትስ ሙሉ በሙሉ በማስጠንቀቂያ ሥር የሚገኙ ሲሆን፣ ጢሱ ወደ ቦስተን አካባቢ በመግባቱ የሰማዩ ቀለም ከነጭ ወደ አስፈሪ ቡናማና ቢጫነት ተቀይሯል። ይህ ቢጫማ ጢስ በቨርሞንት፣ ኒው ሃምፕሻየር እና ሜይን ግዛቶችም ታይቷል።
በሚኒሶታ የብሔራዊ የአየር ሁኔታ አገልግሎት ባለሙያዎች፣ ኅብረተሰቡ ከጢሱ እና ከከፍተኛው ሙቀት ራሱን ለመጠበቅ በተቻለ መጠን በቤት ውስጥ እንዲቆይ መክረዋል። ይህ ከሰደድ እሳቱ የሚወጣው ብክለት የመተንፈስ ችግርን፣ ሳልን፣ ማዞርን ወይም ድካምን ሊያስከትል እንዲሁም ሥር የሰደዱ የጤና እክሎችን ሊያባብስ ይችላል። የሕክምና ባለሙያዎች የውጭ አካባቢ እንቅስቃሴዎችን መቀነስ፣ ወደ ውጭ መውጣት ግዴታ ከሆነ የፊት ጭንብል መጠቀም፣ እና መስኮቶችን በመዝጋት የአየር ማጣሪያዎችን ወይም የአየር ማቀዝቀዣዎችን አብርቶ በመተው የውስጥ አየርን ንጹህ ማድረግ እንደሚገባ ይመክራሉ።
ለዚህ የአየር ብክለት ለረጅም ጊዜ መጋለጥ ወደፊት ሥር ለሰደዱ የጤና እክሎች የመጋለጥ እድልን እንደሚጨምር የሕክምና ባለሙያዎች ያስጠነቅቃሉ። በቅርቡ የወጣ አንድ ጥናት እንደሚያሳየው፣ በአሜሪካ ውስጥ ከሰደድ እሳት ለሚወጣ የአየር ብክለት መጋለጥ በየዓመቱ በአሥር ሺዎች ለሚቆጠሩ ሰዎች ሞት ምክንያት ሆኗል። በኮሎምቢያ ዩኒቨርሲቲ የአየር ንብረት ትምህርት ቤት ባለሙያዎች እንደገለጹት፣ በካናዳ እና አሜሪካ የተፈጠረው ከባድ የድርቅ ሁኔታ ከከፍተኛ ሙቀት ጋር ተዳምሮ ለእነዚህ የሰደድ እሳቶች መባባስ ዋና ምክንያት ሆኗል። በድንጋይ ከሰል፣ በነዳጅ እና በጋዝ አጠቃቀም ምክንያት የሚፈጠረው የሙቀት መጨመር፣ የሰደድ እሳቶቹ በተደጋጋሚ እና በከፍተኛ ኃይል እንዲከሰቱ እያደረገ መሆኑን ጥናቶች ያሳያሉ።
በዚህ ሳምንት መጀመሪያ ላይ በኦንታሪዮ አቅራቢያ የሚገኝ አንድ የጭነት ባቡር በድንገት እየነደደ ባለው የጫካ እሳት ግድግዳ ውስጥ ተከቦ እንደነበር የሚያሳይ አስደንጋጭ ቪዲዮ መውጣቱ ይታወሳል። የባቡሩ ሠራተኞች ሌላ ባቡር እስኪያልፍ ድረስ መንቀሳቀስ ባለመቻላቸው ዙሪያቸው ሲነድ በፍርሃት ለመመልከት ተገደው ነበር። የካናዳ ብሔራዊ የባቡር ሀዲድ በዚያ መስመር ላይ የባቡር ትራንስፖርትን ያቋረጠ ቢሆንም፣ በባቡሩ ውስጥ የነበሩት ሰዎች በሙሉ ግን በሰላም ማለፋቸውን አረጋግጧል።
ከእሳቱ የሚወጣው ከፍተኛ መጠን ያለው ጥቃቅን ብናኝ በተለይም ለሕፃናት፣ እንዲሁም የልብ እና የሳምባ ሕመም ላለባቸው የኅብረተሰብ ክፍሎች እጅግ አደገኛ መሆኑ ተነግሯል። ባለፈው ሐሙስ ዕለት ሚኒያፖሊስ፣ ቺካጎ እና ዲትሮይት በዓለም ላይ ከፍተኛ የአየር ብክለት ካለባቸው አምስት ዋና ዋና ከተሞች ዝርዝር ውስጥ ገብተዋል። የአየር ጥራት ማስጠንቀቂያው ከሚኒሶታ አንስቶ እስከ ሰሜን ምሥራቅ አሜሪካ የተዘረጋ ሲሆን፣ የሚኒሶታ ባለሥልጣናት የትዊን ሲቲስ የሜትሮ አካባቢን ጨምሮ እስከ አርብ የሚቆይ የአየር ጥራት ማስጠንቀቂያ አውጥተዋል። በተለይም በሰሜን ምሥራቅ ሚኒሶታ የአየር ጥራቱ ለማንም ሰው ደኅንነቱ የተጠበቀ ወደማይሆንበት አደገኛ ደረጃ ደርሷል።
በመላው የኒው ዮርክ ግዛት ማሳሰቢያ የወጣ ሲሆን፣ ለተጓዦች የፊት ጭንብል እንደሚከፋፈል ባለሥልጣናት ገልጸዋል። ፔንሲልቬንያ በበኩሏ እጅግ አደገኛ የሆነውን የቀይ ኮድ የአየር ጥራት ማስጠንቀቂያ አስተላልፋለች። በሚቺጋን እና ማሳቹሴትስ ሙሉ በሙሉ በማስጠንቀቂያ ሥር የሚገኙ ሲሆን፣ ጢሱ ወደ ቦስተን አካባቢ በመግባቱ የሰማዩ ቀለም ከነጭ ወደ አስፈሪ ቡናማና ቢጫነት ተቀይሯል። ይህ ቢጫማ ጢስ በቨርሞንት፣ ኒው ሃምፕሻየር እና ሜይን ግዛቶችም ታይቷል።
በሚኒሶታ የብሔራዊ የአየር ሁኔታ አገልግሎት ባለሙያዎች፣ ኅብረተሰቡ ከጢሱ እና ከከፍተኛው ሙቀት ራሱን ለመጠበቅ በተቻለ መጠን በቤት ውስጥ እንዲቆይ መክረዋል። ይህ ከሰደድ እሳቱ የሚወጣው ብክለት የመተንፈስ ችግርን፣ ሳልን፣ ማዞርን ወይም ድካምን ሊያስከትል እንዲሁም ሥር የሰደዱ የጤና እክሎችን ሊያባብስ ይችላል። የሕክምና ባለሙያዎች የውጭ አካባቢ እንቅስቃሴዎችን መቀነስ፣ ወደ ውጭ መውጣት ግዴታ ከሆነ የፊት ጭንብል መጠቀም፣ እና መስኮቶችን በመዝጋት የአየር ማጣሪያዎችን ወይም የአየር ማቀዝቀዣዎችን አብርቶ በመተው የውስጥ አየርን ንጹህ ማድረግ እንደሚገባ ይመክራሉ።
ለዚህ የአየር ብክለት ለረጅም ጊዜ መጋለጥ ወደፊት ሥር ለሰደዱ የጤና እክሎች የመጋለጥ እድልን እንደሚጨምር የሕክምና ባለሙያዎች ያስጠነቅቃሉ። በቅርቡ የወጣ አንድ ጥናት እንደሚያሳየው፣ በአሜሪካ ውስጥ ከሰደድ እሳት ለሚወጣ የአየር ብክለት መጋለጥ በየዓመቱ በአሥር ሺዎች ለሚቆጠሩ ሰዎች ሞት ምክንያት ሆኗል። በኮሎምቢያ ዩኒቨርሲቲ የአየር ንብረት ትምህርት ቤት ባለሙያዎች እንደገለጹት፣ በካናዳ እና አሜሪካ የተፈጠረው ከባድ የድርቅ ሁኔታ ከከፍተኛ ሙቀት ጋር ተዳምሮ ለእነዚህ የሰደድ እሳቶች መባባስ ዋና ምክንያት ሆኗል። በድንጋይ ከሰል፣ በነዳጅ እና በጋዝ አጠቃቀም ምክንያት የሚፈጠረው የሙቀት መጨመር፣ የሰደድ እሳቶቹ በተደጋጋሚ እና በከፍተኛ ኃይል እንዲከሰቱ እያደረገ መሆኑን ጥናቶች ያሳያሉ።
በዚህ ሳምንት መጀመሪያ ላይ በኦንታሪዮ አቅራቢያ የሚገኝ አንድ የጭነት ባቡር በድንገት እየነደደ ባለው የጫካ እሳት ግድግዳ ውስጥ ተከቦ እንደነበር የሚያሳይ አስደንጋጭ ቪዲዮ መውጣቱ ይታወሳል። የባቡሩ ሠራተኞች ሌላ ባቡር እስኪያልፍ ድረስ መንቀሳቀስ ባለመቻላቸው ዙሪያቸው ሲነድ በፍርሃት ለመመልከት ተገደው ነበር። የካናዳ ብሔራዊ የባቡር ሀዲድ በዚያ መስመር ላይ የባቡር ትራንስፖርትን ያቋረጠ ቢሆንም፣ በባቡሩ ውስጥ የነበሩት ሰዎች በሙሉ ግን በሰላም ማለፋቸውን አረጋግጧል።
21 days ago
"በሚሊዮን አንድ ጊዜ የሚከሰት ታሪክ!"
*********
ሊዮኔል ሜሲ እና ላሚን ያማል በ2026ቱ የፊፋ ዓለም ዋንጫ ፍጻሜ ላይ ለመጀመሪያ ጊዜ በአንድ ሜዳ ላይ ለመገናኘት ተዘጋጅተዋል።
ነገር ግን በመካከላቸው ያለው አስገራሚ ግንኙነት የተጀመረው ከሁለት አስርት ዓመታት ገደማ በፊት ነበር።
እ.አ.አ. በታኅሣሥ 2007 የ20 ዓመቱ ወጣት ሊዮኔል ሜሲ ለባርሴሎና ፋውንዴሽን የበጎ አድራጎት ቀን በሚዘጋጅ የፎቶ ግራፍ መርኃ ግብር ላይ ተሳትፎ ነበር።
በወቅቱ ሜሲ አምስት ወር ከሆነው ሕፃን ላሚን ያማል ጋር አብሮ ፎቶ የተነሳ ሲሆን፣ ሕፃኑን በገንዳ ውስጥ ሲያጥበውና ሲንከባከበው የሚያሳዩት እነዚህ ምስሎች ለዩኒሴፍ እና ለሌሎች በጎ አድራጎት ድርጅቶች ገቢ ማሰባሰቢያነት ታትመው ወጥተዋል።
ይህን ታሪካዊ ምስል የቀረጸው ፎቶ ግራፍ አንሺ ጆአን ሞንፎርት በሰጠው አስተያየት፤ በወቅቱ የወደፊቱን ማንም እንዳልገመተው ተናግሯል።
በዚያን ጊዜ ሜሲ የምንግዜም ታላቁ እግር ኳስ ተጫዋች ለመሆን ገና ጉዞውን የጀመረበት ወቅት የነበረ ሲሆን፣ ያማል ደግሞ በፕሮጀክቱ ላይ ከተሳተፉት በርካታ ሕፃናት መካከል አንዱ ነበር።
ይህ ታሪካዊ ፎቶ ግራፍ የመገናኛ ብዙኃንን ትኩረት የሳበው በ2024ቱ የአውሮፓ ዋንጫ ወቅት የያማል አባት በማኅበራዊ ሚዲያ ካጋሩት በኋላ ነበር።
ከዚያ ጊዜ ጀምሮ ምስሉ የሁለቱን የባርሴሎና ትውልድ ኮከቦች የሚወክል የእግር ኳስ ታሪክ ተምሳሌት ሆኗል።
ያማል በ2014 የባርሴሎናውን ላማሲያ አካዳሚን የተቀላቀለ ሲሆን፣ ፈጣን ዕድገት በማሳየት ገና በ15 ዓመቱ ለዋናው ቡድን መጫወት ችሏል።
አሁን ላይ የስፔን እግር ኳስ ትልቁ ተስፋ የሆነው ያማል፣ በባርሴሎና ቤት የሜሲን ታሪካዊ የ10 ቁጥር መለያ የሚለብስ ሲሆን በብዙዎች ዘንድም የሜሲ ተተኪ ተደርጎም ይወሰዳል።
አሁን ግን የእግር ኳስ ታሪክ አስደናቂውን ምዕራፍ ሊያሳየን ተቃርቧል።
በአንድ ወቅት በሜሲ እቅፍ ውስጥ የነበረው ያ ሕፃን፣ አሁን በትልቁ መድረክ ማለትም በዓለም ዋንጫ ፍጻሜ ላይ የልጅነት አርአያውን ፊት ለፊት ለመጋፈጥ እየተዘጋጀ ይገኛል።
ፎቶግራፍ አንሺው ጆአን ሞንፎርት ይህንን ታሪክ "በሚሊዮን አንድ ጊዜ ብቻ የሚከሰት" ሲል ገልጾታል።
በእሱባለው ተሾመ
#worldcup #sports #messi #lamineyamal #ebc
*********
ሊዮኔል ሜሲ እና ላሚን ያማል በ2026ቱ የፊፋ ዓለም ዋንጫ ፍጻሜ ላይ ለመጀመሪያ ጊዜ በአንድ ሜዳ ላይ ለመገናኘት ተዘጋጅተዋል።
ነገር ግን በመካከላቸው ያለው አስገራሚ ግንኙነት የተጀመረው ከሁለት አስርት ዓመታት ገደማ በፊት ነበር።
እ.አ.አ. በታኅሣሥ 2007 የ20 ዓመቱ ወጣት ሊዮኔል ሜሲ ለባርሴሎና ፋውንዴሽን የበጎ አድራጎት ቀን በሚዘጋጅ የፎቶ ግራፍ መርኃ ግብር ላይ ተሳትፎ ነበር።
በወቅቱ ሜሲ አምስት ወር ከሆነው ሕፃን ላሚን ያማል ጋር አብሮ ፎቶ የተነሳ ሲሆን፣ ሕፃኑን በገንዳ ውስጥ ሲያጥበውና ሲንከባከበው የሚያሳዩት እነዚህ ምስሎች ለዩኒሴፍ እና ለሌሎች በጎ አድራጎት ድርጅቶች ገቢ ማሰባሰቢያነት ታትመው ወጥተዋል።
ይህን ታሪካዊ ምስል የቀረጸው ፎቶ ግራፍ አንሺ ጆአን ሞንፎርት በሰጠው አስተያየት፤ በወቅቱ የወደፊቱን ማንም እንዳልገመተው ተናግሯል።
በዚያን ጊዜ ሜሲ የምንግዜም ታላቁ እግር ኳስ ተጫዋች ለመሆን ገና ጉዞውን የጀመረበት ወቅት የነበረ ሲሆን፣ ያማል ደግሞ በፕሮጀክቱ ላይ ከተሳተፉት በርካታ ሕፃናት መካከል አንዱ ነበር።
ይህ ታሪካዊ ፎቶ ግራፍ የመገናኛ ብዙኃንን ትኩረት የሳበው በ2024ቱ የአውሮፓ ዋንጫ ወቅት የያማል አባት በማኅበራዊ ሚዲያ ካጋሩት በኋላ ነበር።
ከዚያ ጊዜ ጀምሮ ምስሉ የሁለቱን የባርሴሎና ትውልድ ኮከቦች የሚወክል የእግር ኳስ ታሪክ ተምሳሌት ሆኗል።
ያማል በ2014 የባርሴሎናውን ላማሲያ አካዳሚን የተቀላቀለ ሲሆን፣ ፈጣን ዕድገት በማሳየት ገና በ15 ዓመቱ ለዋናው ቡድን መጫወት ችሏል።
አሁን ላይ የስፔን እግር ኳስ ትልቁ ተስፋ የሆነው ያማል፣ በባርሴሎና ቤት የሜሲን ታሪካዊ የ10 ቁጥር መለያ የሚለብስ ሲሆን በብዙዎች ዘንድም የሜሲ ተተኪ ተደርጎም ይወሰዳል።
አሁን ግን የእግር ኳስ ታሪክ አስደናቂውን ምዕራፍ ሊያሳየን ተቃርቧል።
በአንድ ወቅት በሜሲ እቅፍ ውስጥ የነበረው ያ ሕፃን፣ አሁን በትልቁ መድረክ ማለትም በዓለም ዋንጫ ፍጻሜ ላይ የልጅነት አርአያውን ፊት ለፊት ለመጋፈጥ እየተዘጋጀ ይገኛል።
ፎቶግራፍ አንሺው ጆአን ሞንፎርት ይህንን ታሪክ "በሚሊዮን አንድ ጊዜ ብቻ የሚከሰት" ሲል ገልጾታል።
በእሱባለው ተሾመ
#worldcup #sports #messi #lamineyamal #ebc
22 days ago
አሐዱ ባንክ 4ኛ ዓመቱን በእንጦጦ የችግኝ ተከላ እና በበጎ አድራጎት ሥራዎች እያከበረ ይገኛል
#ethiopia | አሐዱ ባንክ ወደ ስራ የገባበትን አራተኛ ዓመት የምስረታ በዓል ምክንያት በማድረግ በጉለሌ ክፍለ ከተማ እንጦጦ ተራራ ላይ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር አካሄደ።
ዛሬ ሐምሌ 9 ቀን 2018 ዓ.ም የባንኩ ከፍተኛ አመራሮችና ሰራተኞች በተገኙበት በእንጦጦ ተራራ የአፈር መሸርሸርን ለመከላከልና ብዝሃ ሕይወትን ለመጠበቅ የሚያግዙ ከ600 በላይ አገር በቀል ችግኞች ተተክለዋል።
የአሐዱ ባንክ የማርኬቲንግ እና ኮሚኒኬሽንስ ዳይሬክተር አቶ አብይ መልካ ለዝግጅት ክፍላችን እንደገለጹት፣ በዛሬው እለት ከ600 በላይ የሚሆኑና ለአካባቢው ሥነ-ምህዳር ዘላቂ ጠቀሜታ ያላቸው ሀገር በቀል ችግኞች ተተክለዋል ብለዋል።
ተለይተው ከተተከሉት ዝርያዎች መካከል እንደ ኮሶ፣ ብርብራ፣ ዋንዛ፣ ዝግባ እና ቀረሮ ያሉ እፅዋት የሚገኙበት ሲሆን፣ ይህም ቀደም ሲል በቦታው ላይ በስፋት ይስተዋል የነበረውንና ከፍተኛ የውሃ ፍጆታ የሚጠይቀውን የባህር ዛፍ ተክል በሀገር በቀል ዛፎች ለመተካት ያለመ ነው።
አቶ አብይ አክለውም፣ ባንኩ ችግኞቹን ከመትከል ባለፈ በየሦስት ወሩ ክትትልና እንክብካቤ እንደሚያደርግላቸውና ይህንንም ሥራ ከኢትዮጵያ ቅርስ ባለአደራ ተቋም ጋር በመተባበር በኃላፊነት እያከናወነ እንደሚገኝ ገልጸዋል።
የአሐዱ ባንክ የኩባንያ ሴክሬተሪ እና የዳይሬክተሮች ቦርድ ጽሕፈት ቤት ተወካይ የሆኑት አቶ ቢኒያም አህመድ በበኩላቸው ለዝግጅት ክፍላችን እንደገለጹት፣ ይህ የአካባቢ ጥበቃ እንቅስቃሴ ባንኩ በአምስት ዓመት ስትራቴጂያዊ ዕቅዱ ውስጥ ካካተታቸውና ትኩረት ከሰጣቸው መርሆዎች ጋር ቀጥተኛ ትስስር አለው ብለዋል።
አቶ ቢኒያም እንደገለጹት፣ የችግኝ ተከላው በአንድ ጀንበር ዘመቻ ብቻ የሚያበቃ ሳይሆን፣ ባንኩ በቋሚነት ከተረከበው ቦታ በተጨማሪ በአገር አቀፍ ደረጃ ባሉት ከ108 በላይ በሚሆኑ ቅርንጫፎችም ጭምር በየአካባቢው ተጨባጭ ሁኔታ ተግባራዊ የሚደረግና የባንኩን መሠረታዊ እሴት የሚያንጸባርቅ ዘላቂ ተግባር መሆኑን ገልጸዋል።
ባንኩ ከአካባቢ ጥበቃ በተጨማሪ ዘርፈ ብዙ በሆኑ የማህበራዊ ኃላፊነት ሥራዎች ላይ በንቃት እየተሳተፈ ይገኛል። የማርኬቲንግ ዳይሬክተሩ አቶ አብይ እንደገለጹት፣ ባንኩ በየዓመቱ እንደ መቄዶንያ፣ ጌርጌሴኖን እና የሰበታ ደናግላን ገዳም ላሉ ተቋማት የሚሰጠውን ድጋፍ አጠናክሮ የቀጠለ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት የ204 የሚሆኑ አቅመ-ደካማ ሕፃናትን የትምህርትና የመኖሪያ ወጪዎች በየወሩ በመሸፈን እያሳደገ ይገኛል።
ከዚህም ባሻገር የፊታችን ቅዳሜ ሐምሌ 11 ቀን 2018 ዓ.ም የአሐዱ ባንክ ሠራተኞቹ እና ደንበኞች በተደጋጋሚ የሚሳተፉበት የደም ልገሳ መርሃ ግብር ዘንድሮሞ በተጠናከረ መልኩ እንደሚቀጥል ገልጸዋል።
በአራት ዓመታት የአገልግሎት ዘመኑ ፈጣን ዕድገት እያሳየ የመጣው አሐዱ ባንክ፣ በበጀት ዓመቱ 1.15 ቢሊዮን ብር ያልተጣራ ትርፍ ማስመዝገቡንና በቀጣይም ከኢትዮጵያ ካፒታል ማርኬት ባለሥልጣን ፈቃድ ሲያገኝ ወደ ሰፊ የአክሲዮን ሽያጭ እንቅስቃሴ በመግባት ደንበኞቹንና ባለአክሲዮኖቹን ይበልጥ ተጠቃሚ ለማድረግ ዝግጅት እያጠናቀቀ መሆኑ ይታወሳል።
ጌትነት ተመስገን
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
#greenlegacy #greeninitiative
#indigenoustrees #entotomountain
#gullele #addisababa #ethiopia
#ahadubank #ahadubank4thanniversary
#ethiopia | አሐዱ ባንክ ወደ ስራ የገባበትን አራተኛ ዓመት የምስረታ በዓል ምክንያት በማድረግ በጉለሌ ክፍለ ከተማ እንጦጦ ተራራ ላይ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር አካሄደ።
ዛሬ ሐምሌ 9 ቀን 2018 ዓ.ም የባንኩ ከፍተኛ አመራሮችና ሰራተኞች በተገኙበት በእንጦጦ ተራራ የአፈር መሸርሸርን ለመከላከልና ብዝሃ ሕይወትን ለመጠበቅ የሚያግዙ ከ600 በላይ አገር በቀል ችግኞች ተተክለዋል።
የአሐዱ ባንክ የማርኬቲንግ እና ኮሚኒኬሽንስ ዳይሬክተር አቶ አብይ መልካ ለዝግጅት ክፍላችን እንደገለጹት፣ በዛሬው እለት ከ600 በላይ የሚሆኑና ለአካባቢው ሥነ-ምህዳር ዘላቂ ጠቀሜታ ያላቸው ሀገር በቀል ችግኞች ተተክለዋል ብለዋል።
ተለይተው ከተተከሉት ዝርያዎች መካከል እንደ ኮሶ፣ ብርብራ፣ ዋንዛ፣ ዝግባ እና ቀረሮ ያሉ እፅዋት የሚገኙበት ሲሆን፣ ይህም ቀደም ሲል በቦታው ላይ በስፋት ይስተዋል የነበረውንና ከፍተኛ የውሃ ፍጆታ የሚጠይቀውን የባህር ዛፍ ተክል በሀገር በቀል ዛፎች ለመተካት ያለመ ነው።
አቶ አብይ አክለውም፣ ባንኩ ችግኞቹን ከመትከል ባለፈ በየሦስት ወሩ ክትትልና እንክብካቤ እንደሚያደርግላቸውና ይህንንም ሥራ ከኢትዮጵያ ቅርስ ባለአደራ ተቋም ጋር በመተባበር በኃላፊነት እያከናወነ እንደሚገኝ ገልጸዋል።
የአሐዱ ባንክ የኩባንያ ሴክሬተሪ እና የዳይሬክተሮች ቦርድ ጽሕፈት ቤት ተወካይ የሆኑት አቶ ቢኒያም አህመድ በበኩላቸው ለዝግጅት ክፍላችን እንደገለጹት፣ ይህ የአካባቢ ጥበቃ እንቅስቃሴ ባንኩ በአምስት ዓመት ስትራቴጂያዊ ዕቅዱ ውስጥ ካካተታቸውና ትኩረት ከሰጣቸው መርሆዎች ጋር ቀጥተኛ ትስስር አለው ብለዋል።
አቶ ቢኒያም እንደገለጹት፣ የችግኝ ተከላው በአንድ ጀንበር ዘመቻ ብቻ የሚያበቃ ሳይሆን፣ ባንኩ በቋሚነት ከተረከበው ቦታ በተጨማሪ በአገር አቀፍ ደረጃ ባሉት ከ108 በላይ በሚሆኑ ቅርንጫፎችም ጭምር በየአካባቢው ተጨባጭ ሁኔታ ተግባራዊ የሚደረግና የባንኩን መሠረታዊ እሴት የሚያንጸባርቅ ዘላቂ ተግባር መሆኑን ገልጸዋል።
ባንኩ ከአካባቢ ጥበቃ በተጨማሪ ዘርፈ ብዙ በሆኑ የማህበራዊ ኃላፊነት ሥራዎች ላይ በንቃት እየተሳተፈ ይገኛል። የማርኬቲንግ ዳይሬክተሩ አቶ አብይ እንደገለጹት፣ ባንኩ በየዓመቱ እንደ መቄዶንያ፣ ጌርጌሴኖን እና የሰበታ ደናግላን ገዳም ላሉ ተቋማት የሚሰጠውን ድጋፍ አጠናክሮ የቀጠለ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት የ204 የሚሆኑ አቅመ-ደካማ ሕፃናትን የትምህርትና የመኖሪያ ወጪዎች በየወሩ በመሸፈን እያሳደገ ይገኛል።
ከዚህም ባሻገር የፊታችን ቅዳሜ ሐምሌ 11 ቀን 2018 ዓ.ም የአሐዱ ባንክ ሠራተኞቹ እና ደንበኞች በተደጋጋሚ የሚሳተፉበት የደም ልገሳ መርሃ ግብር ዘንድሮሞ በተጠናከረ መልኩ እንደሚቀጥል ገልጸዋል።
በአራት ዓመታት የአገልግሎት ዘመኑ ፈጣን ዕድገት እያሳየ የመጣው አሐዱ ባንክ፣ በበጀት ዓመቱ 1.15 ቢሊዮን ብር ያልተጣራ ትርፍ ማስመዝገቡንና በቀጣይም ከኢትዮጵያ ካፒታል ማርኬት ባለሥልጣን ፈቃድ ሲያገኝ ወደ ሰፊ የአክሲዮን ሽያጭ እንቅስቃሴ በመግባት ደንበኞቹንና ባለአክሲዮኖቹን ይበልጥ ተጠቃሚ ለማድረግ ዝግጅት እያጠናቀቀ መሆኑ ይታወሳል።
ጌትነት ተመስገን
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
#greenlegacy #greeninitiative
#indigenoustrees #entotomountain
#gullele #addisababa #ethiopia
#ahadubank #ahadubank4thanniversary
22 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) ከዚህ ቀደም የኢራን መደበኛ ጦር በዮርዳኖስ «አዝራቅ» አየር ኃይል የጦር ሰፈር ላይ የድሮን ጥቃቶችን መፈጸሙን መዘገባችን ይታወሳል። አሁን ደግሞ የኢራን አብዮታዊ ጠባቂ ጦር በተመሳሳይ የጦር ሰፈር ላይ በሚሳኤል የታገዘ ጥቃት ማድረሱን አስታውቋል።
አብዮታዊ ጠባቂ ጦሩ ለዮርዳኖስ ሕዝብ ባስተላለፈው መልእክት፣ ኃይሎቹ "በዮርዳኖስ አል-አዝራቅ በሚገኘው እጅግ ግዙፍ የጦር ሰፈር ውስጥ የሚገኘውን የአሜሪካ የጦር አውሮፕላኖች ማቆሚያ እና አዲሱን የአሜሪካ የምዕራብ እስያ የዕዝ እና ቁጥጥር ማዕከል 'ካይበር-ሻካን' በተሰኙ ባሊስቲክ ሚሳኤሎች ኢላማ በማድረግ አውድመዋል" ሲል ገልጿል።
ጥቃቱ የተፈጸመው፣ በአህቫዝ ከተማ 121 የካንሰር ታማሚ ሕፃናት ከመጠለያቸው እንዲፈናቀሉ ላደረገው የአሜሪካ ጥቃት፣ እንዲሁም በመጋቢት ወር በሚናብ (ከተማ በሚገኝ ትምህርት ቤት ውስጥ 168 ሕፃናትን ለገደለው የአሜሪካ ጥቃት የአጸፋ እርምጃ (ብቀላ) መሆኑን ጦሩ አስታውቋል። በመሆኑም የዮርዳኖስ ሕዝብ መሬቱ "በሕፃናት ላይ ለሚፈጸሙ እንደዚህ ዓይነት ወንጀሎች" መገልገያ እንዲሆን እንዳይፈቅድ አሳስቧል።
የኢራን አብዮታዊ ጠባቂ ጦር ይህንን መግለጫ ያወጣው፣ የዮርዳኖስ ጦር ዛሬ ማለዳ 8 የኢራን ሚሳኤሎችን በአየር ላይ ማክሸፉን (intercept ማድረጉን) ማስታወቁን ተከትሎ ነው።
አብዮታዊ ጠባቂ ጦሩ ለዮርዳኖስ ሕዝብ ባስተላለፈው መልእክት፣ ኃይሎቹ "በዮርዳኖስ አል-አዝራቅ በሚገኘው እጅግ ግዙፍ የጦር ሰፈር ውስጥ የሚገኘውን የአሜሪካ የጦር አውሮፕላኖች ማቆሚያ እና አዲሱን የአሜሪካ የምዕራብ እስያ የዕዝ እና ቁጥጥር ማዕከል 'ካይበር-ሻካን' በተሰኙ ባሊስቲክ ሚሳኤሎች ኢላማ በማድረግ አውድመዋል" ሲል ገልጿል።
ጥቃቱ የተፈጸመው፣ በአህቫዝ ከተማ 121 የካንሰር ታማሚ ሕፃናት ከመጠለያቸው እንዲፈናቀሉ ላደረገው የአሜሪካ ጥቃት፣ እንዲሁም በመጋቢት ወር በሚናብ (ከተማ በሚገኝ ትምህርት ቤት ውስጥ 168 ሕፃናትን ለገደለው የአሜሪካ ጥቃት የአጸፋ እርምጃ (ብቀላ) መሆኑን ጦሩ አስታውቋል። በመሆኑም የዮርዳኖስ ሕዝብ መሬቱ "በሕፃናት ላይ ለሚፈጸሙ እንደዚህ ዓይነት ወንጀሎች" መገልገያ እንዲሆን እንዳይፈቅድ አሳስቧል።
የኢራን አብዮታዊ ጠባቂ ጦር ይህንን መግለጫ ያወጣው፣ የዮርዳኖስ ጦር ዛሬ ማለዳ 8 የኢራን ሚሳኤሎችን በአየር ላይ ማክሸፉን (intercept ማድረጉን) ማስታወቁን ተከትሎ ነው።
27 days ago
💎 ወርቃማ ክረምት ለልጅዎ ከዮቶጵያ
ዮቶጵያ የሕጻናትና ታደጊዎች ሁለንተናዊ ብቃት ካምፕ፤
👫 ልጅዎን 2 ወራት ከእኛ ጋር እንዲያሳልፍ ያድርጉ፤ በትክክል የማይቆጩበት ውሳኔ ይሆናል፤
👉 በቆይታቸው፤
🧠 የአእምሮ ምህንድስና፣
🏃♂አካል ብቃትና መዝናኛ
⛪️🕌 እንደየ እምነታቸው ስነ ምግባር እና ሃይማኖታዊ እውቀት የሚያገኙበት መንፈሳዊ ትምህርትን ያገኛሉ።
🗓 በሳምንት 5 ቀናት ይቆያሉ፤
ጠዋት በትምርህት ከሰዓት በጨዋታ እና የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ደስ ብሏቸው ያሳልፋሉ።
🏥 አስተማማኝ ጥበቃና የነርስ ባለሙያዎች ተዘጋጅተዋል፤ የልጅዎን ሳምንታዊ እድገትም መከታተል ይችላሉ።
🎁 ከ2 በላይ ልጆች ለሚያስመዘግቡ የ10% ቅናሽ ይደረግላቸዋል፣ ያሉን ቦታዎች ውስን በመሆናቸው ልጅዎን ቀድመው ያስመዝግቡ!።
📍የስልጠና ቦታዎች፤
ቁጥር. 1 ብስራተ ገብርኤል
ቁጥር. 2 አያት አደባባይ ወደ ጣፎ በሚወስደው መንገድ
📲 ለምዝገባ በ0963999966 / 0963999977
ይደውሉ፤
ትክክለኛ የክረምት ምርጫ ለልጅዎ
ከዮቶጵያ የሕፃናትና ታዳጊዎች ሁለንተናዊ የብቃት ካምፕ !!!!
ዮቶጵያ የሕጻናትና ታደጊዎች ሁለንተናዊ ብቃት ካምፕ፤
👫 ልጅዎን 2 ወራት ከእኛ ጋር እንዲያሳልፍ ያድርጉ፤ በትክክል የማይቆጩበት ውሳኔ ይሆናል፤
👉 በቆይታቸው፤
🧠 የአእምሮ ምህንድስና፣
🏃♂አካል ብቃትና መዝናኛ
⛪️🕌 እንደየ እምነታቸው ስነ ምግባር እና ሃይማኖታዊ እውቀት የሚያገኙበት መንፈሳዊ ትምህርትን ያገኛሉ።
🗓 በሳምንት 5 ቀናት ይቆያሉ፤
ጠዋት በትምርህት ከሰዓት በጨዋታ እና የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ደስ ብሏቸው ያሳልፋሉ።
🏥 አስተማማኝ ጥበቃና የነርስ ባለሙያዎች ተዘጋጅተዋል፤ የልጅዎን ሳምንታዊ እድገትም መከታተል ይችላሉ።
🎁 ከ2 በላይ ልጆች ለሚያስመዘግቡ የ10% ቅናሽ ይደረግላቸዋል፣ ያሉን ቦታዎች ውስን በመሆናቸው ልጅዎን ቀድመው ያስመዝግቡ!።
📍የስልጠና ቦታዎች፤
ቁጥር. 1 ብስራተ ገብርኤል
ቁጥር. 2 አያት አደባባይ ወደ ጣፎ በሚወስደው መንገድ
📲 ለምዝገባ በ0963999966 / 0963999977
ይደውሉ፤
ትክክለኛ የክረምት ምርጫ ለልጅዎ
ከዮቶጵያ የሕፃናትና ታዳጊዎች ሁለንተናዊ የብቃት ካምፕ !!!!
Sponsored by
Surafel
Comments