3 months ago
የምርጫ ቅስቀሳ ወይስ የሰርከስ ትርዒት?
#ethiopia | በኔዘርላንድስ ዛሬ ረቡዕ እየተካሄደ በሚገኘው የከተማ ከንቲባዎችና የምክር ቤት አባላት ምርጫ፣ መራጮች በነቂስ ወጥተው ድምፃቸውን እንዲሰጡ ለማበረታታት አንድ ለየት ያለ የምረጡኝ ዘመቻ ቀርቧል። በሮተርዳም ከተማ ለከንቲባነት እየተወዳደሩ የሚገኙት የ48 ዓመቷ እመት ካሮላ ሾውተን፣ መራጮች ያላቸውን የመሳተፍ ፍላጎት ለማነቃቃት ሲሉ የገቡት ቃል በብዙዎች ዘንድ መነጋገሪያ ሆኗል።
የከፍታ ፍርሃትና የድፍረት ውርርድ
እመት ካሮላ ሾውተን ከፍተኛ የከፍታ ፍርሃት (Phobia) እንዳለባቸው በይፋ ቢናገሩም፣ የመራጮች ቁጥር ከቀደመው ጊዜ የተሻለ ሆኖ ከተገኘ ግን ይህንን ፍርሃታቸውን ተቋቁመው ለየት ያለ ተግባር ለመፈጸም ቃል ገብተዋል፦
* ፈተናው፦ በሮተርዳም ከተማ የሚገኘውንና 185 ሜትር ቁመት ያለውን ዝነኛውን የዩሮ ማስት (Euromast) ማማ መውጣት።
* ውርርዱ፦ ማማውን መውጣት ብቻ ሳይሆን፣ በገመድ ተንጠልጥሎ ቁልቁል በመውረድ ድፍረታቸውን ለማሳየት ተስማምተዋል።
የመራጮች ቁጥር መቀነስ ስጋት
በኔዘርላንድስ ባለፈው የምርጫ ወቅት የታየው የመራጮች ተሳትፎ 38.9 በመቶ ብቻ የነበረ ሲሆን፣ ይህም በአገሪቱ የምርጫ ታሪክ ዝቅተኛው ተብሎ ተመዝግቧል። ያሁ ኒውስን ዋቢ በማድረግ ትርታ እንደዘገበው፣ እመት ካሮላ ይህንን ዝቅተኛ ቁጥር ከፍ ለማድረግና ዜጎች ለዴሞክራሲያዊ መብታቸው ትኩረት እንዲሰጡ ለማድረግ የገቡት ይህ ውርርድ በዛሬው ምርጫ ውጤት ላይ ምን ዓይነት ለውጥ እንደሚያመጣ ይጠበቃል።
ምርጫው ተጠናቆ የመራጮች ቁጥር ማሻቀቡ ከተረጋገጠ፣ የሮተርዳም ከንቲባ ዕጩ ካሮላ ሾውተን ከአውሮጳ ረጅሙ ከሚባለው ማማ ላይ በገመድ ተንጠልጥለው ሲወርዱ የምናይ ይሆናል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #tirtafm #netherlands #rotterdam #election2026 #carolaschouten #euromast #democracy #voting #worldnews
#ethiopia | በኔዘርላንድስ ዛሬ ረቡዕ እየተካሄደ በሚገኘው የከተማ ከንቲባዎችና የምክር ቤት አባላት ምርጫ፣ መራጮች በነቂስ ወጥተው ድምፃቸውን እንዲሰጡ ለማበረታታት አንድ ለየት ያለ የምረጡኝ ዘመቻ ቀርቧል። በሮተርዳም ከተማ ለከንቲባነት እየተወዳደሩ የሚገኙት የ48 ዓመቷ እመት ካሮላ ሾውተን፣ መራጮች ያላቸውን የመሳተፍ ፍላጎት ለማነቃቃት ሲሉ የገቡት ቃል በብዙዎች ዘንድ መነጋገሪያ ሆኗል።
የከፍታ ፍርሃትና የድፍረት ውርርድ
እመት ካሮላ ሾውተን ከፍተኛ የከፍታ ፍርሃት (Phobia) እንዳለባቸው በይፋ ቢናገሩም፣ የመራጮች ቁጥር ከቀደመው ጊዜ የተሻለ ሆኖ ከተገኘ ግን ይህንን ፍርሃታቸውን ተቋቁመው ለየት ያለ ተግባር ለመፈጸም ቃል ገብተዋል፦
* ፈተናው፦ በሮተርዳም ከተማ የሚገኘውንና 185 ሜትር ቁመት ያለውን ዝነኛውን የዩሮ ማስት (Euromast) ማማ መውጣት።
* ውርርዱ፦ ማማውን መውጣት ብቻ ሳይሆን፣ በገመድ ተንጠልጥሎ ቁልቁል በመውረድ ድፍረታቸውን ለማሳየት ተስማምተዋል።
የመራጮች ቁጥር መቀነስ ስጋት
በኔዘርላንድስ ባለፈው የምርጫ ወቅት የታየው የመራጮች ተሳትፎ 38.9 በመቶ ብቻ የነበረ ሲሆን፣ ይህም በአገሪቱ የምርጫ ታሪክ ዝቅተኛው ተብሎ ተመዝግቧል። ያሁ ኒውስን ዋቢ በማድረግ ትርታ እንደዘገበው፣ እመት ካሮላ ይህንን ዝቅተኛ ቁጥር ከፍ ለማድረግና ዜጎች ለዴሞክራሲያዊ መብታቸው ትኩረት እንዲሰጡ ለማድረግ የገቡት ይህ ውርርድ በዛሬው ምርጫ ውጤት ላይ ምን ዓይነት ለውጥ እንደሚያመጣ ይጠበቃል።
ምርጫው ተጠናቆ የመራጮች ቁጥር ማሻቀቡ ከተረጋገጠ፣ የሮተርዳም ከንቲባ ዕጩ ካሮላ ሾውተን ከአውሮጳ ረጅሙ ከሚባለው ማማ ላይ በገመድ ተንጠልጥለው ሲወርዱ የምናይ ይሆናል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #tirtafm #netherlands #rotterdam #election2026 #carolaschouten #euromast #democracy #voting #worldnews
6 months ago
ሞቃዲሾ ምርጫ ስታደርግ ዋለች
#ethiopia | የብሪታኒያ ሶማሊላንድ እና የኢጣሊያ ሶማሊላንድ በሚል ለሁለት ተከፍላ በቅኝ ስትተዳደር የነበረችው ሶማሊያ ነጻነቷን ካገኘችበት 1960 ወዲህ ለተከታይ ዓመታት መደበኛ ምርጫን ስታደር ቆይታለች።
በ1969 የተደረገው ምርጫ ከተከወነ ከወራት በኋላ ወታደራዊ አዛዡ ጄነራል ሞሐመድ ሰዒድ ባሬ የመሩትን መፈንቅለ-መንግሥት ተከትሎ እርሣቸው በሥልጣን ላይ እስከቆዩበት 1991 ድረስ ሶማሊያ በወታደራዊ አገዛዝ ስር ከርማለች።
እርሣቸው ከሥልጣን ከተነሱ በኋላ በጎሣ እና ኃይማኖት በተከፋፈሉ ታጣቂዎች ስትታመስ የቆየችው ሶማሊያ፣ በ2004 የጎሣ ተወካዮች በሚሠጡት ድምጽ መሪዎቿን ስትመርጥም ቆይታ ነበር።
ከዚህ ዓመት ጀምሮ ግን ይህን የምርጫ መንገድ በመተው ቀጥተኛ ምርጫን ለማድረግ በተወሰነው መሠረት በመዲናዋ ሞቃዲሾ ድምጽ ሲሰጥ መዋሉን ያስነበበው ኢስት አፍሪቃ ኒውስ ነው ሲል። #tirtafm
#ethiopia | የብሪታኒያ ሶማሊላንድ እና የኢጣሊያ ሶማሊላንድ በሚል ለሁለት ተከፍላ በቅኝ ስትተዳደር የነበረችው ሶማሊያ ነጻነቷን ካገኘችበት 1960 ወዲህ ለተከታይ ዓመታት መደበኛ ምርጫን ስታደር ቆይታለች።
በ1969 የተደረገው ምርጫ ከተከወነ ከወራት በኋላ ወታደራዊ አዛዡ ጄነራል ሞሐመድ ሰዒድ ባሬ የመሩትን መፈንቅለ-መንግሥት ተከትሎ እርሣቸው በሥልጣን ላይ እስከቆዩበት 1991 ድረስ ሶማሊያ በወታደራዊ አገዛዝ ስር ከርማለች።
እርሣቸው ከሥልጣን ከተነሱ በኋላ በጎሣ እና ኃይማኖት በተከፋፈሉ ታጣቂዎች ስትታመስ የቆየችው ሶማሊያ፣ በ2004 የጎሣ ተወካዮች በሚሠጡት ድምጽ መሪዎቿን ስትመርጥም ቆይታ ነበር።
ከዚህ ዓመት ጀምሮ ግን ይህን የምርጫ መንገድ በመተው ቀጥተኛ ምርጫን ለማድረግ በተወሰነው መሠረት በመዲናዋ ሞቃዲሾ ድምጽ ሲሰጥ መዋሉን ያስነበበው ኢስት አፍሪቃ ኒውስ ነው ሲል። #tirtafm
6 months ago
ፍቅር እስከ ባህር
#ethiopia | በምዕራባውያን አቆጣጠር 2011 ጃፓናውያን አስከፊ በሆነ ሱናሚ የተባለ የባህር ወጀብ ተመቱ፡፡ ያ ሱናሚ ሊገመትም እንደሚቻለው የብዙዎችን ሕይወት ቀጠፈ፣ ቤቶች ብቻ ሳይሆን መንደሮችን አፈራረሰ፡፡ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችም የደረሱበት ሳይታወቅ ጠፍተዋል፡፡
ታዲያ በሱናሚው ምክንያት የደረሱበት ከጠፋ ሰዎች መሃከል የአንዱ ቤተሰብ ታሪክ፣ ይኼው ዛሬ ከአደጋው 14 ዓመታት በኋላም መነጋገሪያ ሆኖ ዘልቋል፡፡
ነገሩ እንዲህ ነው…
የባንክ ባለሙያዋ ዩኮ እና የልዩ ጥበቃ አባል ወታደሩ ያሱዎ ባለትዳሮች ናቸው፡፡ በ1988 የተመሠረተው ትዳራቸው ለአካባቢው ሰው ሁሉ ምሣሌ ነበር፡፡ አንድ ዕለት ያሱዎ፣ ባለቤቱ ዩኮን እስከ መሥሪያ ቤቷ በር ያደርሳትና፣ የሚስቱን እናት አማቹን ደግሞ በዕለቱ ለነበራቸው የሕክምና ክትትል ሐኪም ቤት ወሰዳቸው፡፡
እርሣቸውን ሐኪም ቤት አስገብቶ ወደ ሥራው ለመኼድ መንገድ ከጀመረ ከአፍታ በኋላ ግን፤ ለስድስት ደቂቃዎች የዘለቀ ከባድ ርዕደ-መሬት ተከሰተ፡፡ ያሱዎ በመኪናው ውስጥ ያለውን ሬዲዮ ሲከፍት ርዕደ-መሬቱ ከበድ ያለ ሱናሚ ማስከተሉ እየተዘገበ አደመጠ፡፡
ይህን ሲሰማ አስቀድሞ ወደ ወንድ ልጁ ደወለ፤ ደህና እንደሆነም አረጋገጠ፡፡ የባለቤቱ እና ሴት ልጁን ሥልክ መስመር ግን ሊያገኝ አልቻለም፡፡ አንድ ሊያገኝ የቻለው ነገር ባለቤቱ በደምጽ የተወችለት መልዕክት ነው፡፡
‹‹አስፈሪ ሁናቴ ውስጥ ነኝ፤ ቶሎ ወደቤቴ መመለስ እፈልጋለሁ፡፡›› ይላል፡፡
ያሱዎ የባለቤቱን ዳና ፍለጋ በሆስፒታል፣ መጠለያ ጣቢያ ሁሉ ተሰማራ፡፡ ምንም ሊያገኝ አልቻለም፤ ከአንድ ወር በኋላ የሚስትህ ዩኮ የእጅ ሥልክ ተገኝቷል ተብሎ ተጠራ፡፡ ሥልኳ ላይ ‹‹ሱናሚው እጅግ ያስፈራል›› የሚል መልዕክት ጽፋ የነበረ ቢሆንም ለእርሡ አልደረሰውም፡፡ ከዚህ በቀር ሚስቴን አፋልጉኝ ብሎ በየቦታው ቢፈልግ አንዳችም መረጃ ሳይሰማ ቀናት፣ ሣምንታት፣ ወራት አለፉ፡፡
ይኼው ዘንድሮ 14 ዓመታቸው፡፡
ያሱዎ ግን ተሥፋ አልቆረጠም፡፡ ዜናውን የነገረን ዴይሊ ሚረር እንደዘገበው አቶ ያሱዎ ላለፉት 14 ዓመታት 50 እና 60 ሜትር ድረስ ጥልቀት ያለው ባህር ውስጥ ጭምር ከ400 ጊዜያት በላይ ዋኝቶ ሚስቱን እየፈለገ ነው፡፡
ስለተግባሩ ለጠየቁትም
መፈለግ እኔ መች ሰለቸኝ፣ ገና ብዙ ይቀረኛል
ሚስቴን እስካገኝ ድረስ መቼ ድካም ይሰማኛል
ብሏል አሉ፡፡
#tirtafm
#ethiopia | በምዕራባውያን አቆጣጠር 2011 ጃፓናውያን አስከፊ በሆነ ሱናሚ የተባለ የባህር ወጀብ ተመቱ፡፡ ያ ሱናሚ ሊገመትም እንደሚቻለው የብዙዎችን ሕይወት ቀጠፈ፣ ቤቶች ብቻ ሳይሆን መንደሮችን አፈራረሰ፡፡ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችም የደረሱበት ሳይታወቅ ጠፍተዋል፡፡
ታዲያ በሱናሚው ምክንያት የደረሱበት ከጠፋ ሰዎች መሃከል የአንዱ ቤተሰብ ታሪክ፣ ይኼው ዛሬ ከአደጋው 14 ዓመታት በኋላም መነጋገሪያ ሆኖ ዘልቋል፡፡
ነገሩ እንዲህ ነው…
የባንክ ባለሙያዋ ዩኮ እና የልዩ ጥበቃ አባል ወታደሩ ያሱዎ ባለትዳሮች ናቸው፡፡ በ1988 የተመሠረተው ትዳራቸው ለአካባቢው ሰው ሁሉ ምሣሌ ነበር፡፡ አንድ ዕለት ያሱዎ፣ ባለቤቱ ዩኮን እስከ መሥሪያ ቤቷ በር ያደርሳትና፣ የሚስቱን እናት አማቹን ደግሞ በዕለቱ ለነበራቸው የሕክምና ክትትል ሐኪም ቤት ወሰዳቸው፡፡
እርሣቸውን ሐኪም ቤት አስገብቶ ወደ ሥራው ለመኼድ መንገድ ከጀመረ ከአፍታ በኋላ ግን፤ ለስድስት ደቂቃዎች የዘለቀ ከባድ ርዕደ-መሬት ተከሰተ፡፡ ያሱዎ በመኪናው ውስጥ ያለውን ሬዲዮ ሲከፍት ርዕደ-መሬቱ ከበድ ያለ ሱናሚ ማስከተሉ እየተዘገበ አደመጠ፡፡
ይህን ሲሰማ አስቀድሞ ወደ ወንድ ልጁ ደወለ፤ ደህና እንደሆነም አረጋገጠ፡፡ የባለቤቱ እና ሴት ልጁን ሥልክ መስመር ግን ሊያገኝ አልቻለም፡፡ አንድ ሊያገኝ የቻለው ነገር ባለቤቱ በደምጽ የተወችለት መልዕክት ነው፡፡
‹‹አስፈሪ ሁናቴ ውስጥ ነኝ፤ ቶሎ ወደቤቴ መመለስ እፈልጋለሁ፡፡›› ይላል፡፡
ያሱዎ የባለቤቱን ዳና ፍለጋ በሆስፒታል፣ መጠለያ ጣቢያ ሁሉ ተሰማራ፡፡ ምንም ሊያገኝ አልቻለም፤ ከአንድ ወር በኋላ የሚስትህ ዩኮ የእጅ ሥልክ ተገኝቷል ተብሎ ተጠራ፡፡ ሥልኳ ላይ ‹‹ሱናሚው እጅግ ያስፈራል›› የሚል መልዕክት ጽፋ የነበረ ቢሆንም ለእርሡ አልደረሰውም፡፡ ከዚህ በቀር ሚስቴን አፋልጉኝ ብሎ በየቦታው ቢፈልግ አንዳችም መረጃ ሳይሰማ ቀናት፣ ሣምንታት፣ ወራት አለፉ፡፡
ይኼው ዘንድሮ 14 ዓመታቸው፡፡
ያሱዎ ግን ተሥፋ አልቆረጠም፡፡ ዜናውን የነገረን ዴይሊ ሚረር እንደዘገበው አቶ ያሱዎ ላለፉት 14 ዓመታት 50 እና 60 ሜትር ድረስ ጥልቀት ያለው ባህር ውስጥ ጭምር ከ400 ጊዜያት በላይ ዋኝቶ ሚስቱን እየፈለገ ነው፡፡
ስለተግባሩ ለጠየቁትም
መፈለግ እኔ መች ሰለቸኝ፣ ገና ብዙ ይቀረኛል
ሚስቴን እስካገኝ ድረስ መቼ ድካም ይሰማኛል
ብሏል አሉ፡፡
#tirtafm
6 months ago
በጢሙ ፊደል አስቆጣሪው
#ethiopia | በወል ትስስር ገጾቻቸው ትኩረት፣ ዕይታን ፍለጋ ሰዎች ምንም ከማድረግ የሚመለሱ አይመስለንም ያሉት የኤን ዲ ቴቪ ዘጋቢዎች እንግሊዛዊው ሰውዬም እንዲሁ ነው ብለውናል፡፡
በገጽ ሥሙ ሞቬምበር ዩኬ የተሰኘው ግለሰብ አንድ ዕለት በወል መገናኛ ትስስር ገጹ ካሜራውን ደግኖ ቀረበ፤ ከዚያም ጺሙን በእንግሊዘኛው A ፊደል ቅርጽ ከረከመው፡፡
እንዲህ እያለ በተከታታይ ሙሉ የእንግሊዘኛ ፊደል ተራን ቅርጽ ጺሙን እየተቆረጠም ከ2.5 ሚልየን በላይ ተከታዮችን እንዳፈራ ኤን ዲ ቴቪ አስነብቧል፡፡
ግለሰቡ ይህን ማድረጉ ያስደነቃቸው ተከታዮቹ ሰውዬው በአንድ ፊደል ቅርጽ ተከርክሞ፣ እንደገና ጺሙ እስኪበቅል መጠበቅና፣ ዳግም በሌላ ፊደል ቅርጽ ለመከርከም ያሳየውን ቁርጠኝነት ‹‹ጀግናስ እንዳንተ ያለው እንጂ›› የሚል ዓይነት ሙገሳ ከማዥጎድጎዳቸው ባለፈ፣ ‹‹ምን ያህል ጊዜ ፈጀብህ?›› እያሉ የጠየቁም እንዳሉ በዜናው ላይ ተጠቅሶ አስተውለናል፡፡
#tirtafm
#ethiopia | በወል ትስስር ገጾቻቸው ትኩረት፣ ዕይታን ፍለጋ ሰዎች ምንም ከማድረግ የሚመለሱ አይመስለንም ያሉት የኤን ዲ ቴቪ ዘጋቢዎች እንግሊዛዊው ሰውዬም እንዲሁ ነው ብለውናል፡፡
በገጽ ሥሙ ሞቬምበር ዩኬ የተሰኘው ግለሰብ አንድ ዕለት በወል መገናኛ ትስስር ገጹ ካሜራውን ደግኖ ቀረበ፤ ከዚያም ጺሙን በእንግሊዘኛው A ፊደል ቅርጽ ከረከመው፡፡
እንዲህ እያለ በተከታታይ ሙሉ የእንግሊዘኛ ፊደል ተራን ቅርጽ ጺሙን እየተቆረጠም ከ2.5 ሚልየን በላይ ተከታዮችን እንዳፈራ ኤን ዲ ቴቪ አስነብቧል፡፡
ግለሰቡ ይህን ማድረጉ ያስደነቃቸው ተከታዮቹ ሰውዬው በአንድ ፊደል ቅርጽ ተከርክሞ፣ እንደገና ጺሙ እስኪበቅል መጠበቅና፣ ዳግም በሌላ ፊደል ቅርጽ ለመከርከም ያሳየውን ቁርጠኝነት ‹‹ጀግናስ እንዳንተ ያለው እንጂ›› የሚል ዓይነት ሙገሳ ከማዥጎድጎዳቸው ባለፈ፣ ‹‹ምን ያህል ጊዜ ፈጀብህ?›› እያሉ የጠየቁም እንዳሉ በዜናው ላይ ተጠቅሶ አስተውለናል፡፡
#tirtafm
Sponsored by
Surafel
Comments