3 months ago
የካፒታል ገበያ እና መዋለ ንዋይ ሰነድ
በኢትዮጵያ ህግ ማእቀፍ
የኢትዮጲያ ካፒታል አዋጅ ቁጥር 1248/13
ጠበቃና የህግ አማካሪ ፋንታሁን ደለለው
መግቢያ #ethiopia | የካፒታል ገበያ በኢትዮጵያ በህግ ማእቀፍ ተደግፎ የመዋለ ሰነዶችን ሽያጭ በማሳደግ ረገድ ሀገራችን የካፒታል አዋጅ ቁጥር 1248/13 አውጥቶ በስራ ላይ መዋሉ የእነዚህ ሰነዶችን ሽያጭ ገበያ በመፍጠር ኢንቨስተሮችን ከመሳብ ፣ የንግድ ማህበራትን፣ባንኮችን ከማሳደግ፣ የሀገሪቱን የኢኮኖሚ እድገት ከፍ ከማድረግ አንጻር ዘርፈ ብዙ የተሳለጠ የንግድ ትስስር የሚፈጥር ሲሆን በዚህ ጽሁፍ ከህግ ጋር ተያይዞ ያለውን ይዘት ለማህበረሰቡ ግንዛቤ ለመስጠት ይህን ጽሁፍ ወደ እናንተ አቅርበናል።
1. የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ታሪካዊ ዳራ
ኢትዮጵያ ብዙ የህግ ታሪክ ስለ ካፒታል ገበያ እንደሌሎች ሀገራት እንደሌላት የተለያዩ ስለካፒታል ገበያ የተመለከቱ የኢትዮጵያን ታሪክ መመልከት የሚቻል ነው። የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ታሪካዊ ዳራን ስናጤን በአጼ ዘመነ መንግስት እ.ኤ.አ በ1867 ዓ.ም በአጼ ሚኒሊክ ዘመነ መንግስት የኢትዮ ጅቡቲን ሀዲድ ለመዘርጋት የ40 ሚሊዮን ፍራንክ አክስዮን በፈረንሳይ ሀገር መሸጣቸው ታሪክ ያወሳል።በእሳቸው ዘመን የተቋቋመው የመጀመርያው ባንክ፣ አቢሲኒያ ባንክ ሲመሠረት አክሲዮኖቹ ከአዲስ አበባ በተጨማሪ ኒውዮርክ፣ ፓሪስ፣ ለንደንና ቪየና እንደተሸጡ የታሪክ ድርሳናት ያስረዳሉ፡፡
እ.ኤ.አ. በ1956 የኢትዮጵያ የቄራዎች ድርጅት ለሕዝብ ሽያጭ የወጣ ሲሆን፣ እሱን ተከትሎ እ.ኤ.አ. ከ1957 እስከ 1963 ባለው ጊዜ ውስጥ የኢትዮጵያ ጠርሙስ ፋብሪካ (Ethiopian Bottling Company)፣ ኢንዶ-ኢትዮጵያን ጨርቃ ጨርቅ፣ ኤችቪኤ ኢትዮጵያ፣ ሳባ ጠጅ፣ ተንዳሆ ተክልና የአዲስ አበባ ባንክ ለሕዝብ ሽያጭ መውጣታቸውን ለማወቅ ተችሏል፡፡ በተጨማሪ እ.ኤ.አ. በ1959 ወንጂ ስኳር ፋብሪካ ለሕዝብ ሽያጭ የቀረበ ድርጅት መሆኑንና በወቅቱ በሦስት ወራት ውስጥ ከአክሲዮን ሽያጭ 2.5 ሚሊዮን ዶላር መሰብሰብ የተቻለ ሲሆን፣ ኤችቪኤ የተባለው የሆላንድ ኩባንያ አብዛኛውን አክሲዮን መግዛቱ ይነገራል፡፡ እንዲሁም ሕዝቡም ቀላል ሊባል በማይችል መልኩ በግብይት መሳተፉንና ድርሻ መግዛቱን ጄዲቮን ፒስኬ የተባለ ጸሐፊ፣ «አክሲዮንና የአክሲዮን ግብይት በአዲስ አበባ» በሚለው መጽሐፉ ከትቦት ይገኛል።
በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዘመነ መንግሥት በ1960 ዓ.ም. በኢትዮጵያ መንግሥት ባንክ (State Bank of Ethiopia) ውስጥ የአክሲዮን ግብይት መምርያ መቋቋሙ የአክሲዮን ግብይቱን ለማሳደግ ከፍተኛ ሚና ተጫውቷል፡፡ ይህንን መምርያ ማደራጀት የአክሲዮን ገበያን ለማስፋፋት በመንግሥት የተወሰደ የመጀመርያው ተቋማዊ አደረጃጀት ዕርምጃ እንደሆነ ይነገራል፡፡ በወቅቱ የተለያዩ ኢንቨስተሮችን በግብይት በማሳተፍና ዋጋ እንዲሰጡ በማድረግ፣ እንዲሁም በተለያዩ መንገዶች ዋጋ እንዲወሰን ይደረግ ነበር፡፡
እ.ኤ.አ. በ1965 የአክሲዮን ግብይት እያደገ በመሄዱ፣ የሕዝብን እምነት በማግኘቱ፣ ኢኮኖሚውም ዕድገት በማሳየቱ፣ አዳዲስ ኀይለስላሴ ዘመነመንግስት የካፒታል ገበያ የህግ ማእቀፍ ኖሮት የተለያዩ አስፈጻሚ ተቋሟት የማቋቋም የማደራጀት እና የመነቃቃት ስራዎች ተሞክረዋል። ታላቁ የህዳሴ ግድብ ለመገንባት በተደረገው ህዝባዊ ንቅናቄም ብዙ የቦንድ ሽያጭ ለዜጎች፣ ሀገር በቀል ድርጅቶች ፣ ለትውልደ ኢትዮጲያን ፣ ዲያስፖራ ለሌሎችም ተሳታፊ አካላት ተሽጦ በብዙ ቢሊዮን ብር ተሰብስቦ ታላቁን ህዳሴ ግድብ ተገንብቷል።
ይህ ህጉ ከመውጣቱ በፊት ባልተማከለ አሰራር የተፈጸመ ቢሆንም የካፒታል ገበያ ስረአት እጅግ አስፈላጊ መሆኑን ያሳያል። ከዚህም ባለፈ የገበያ መር ስረአት የሚደግፍ ሲሆን ለነጋዴዎች፣ለባለሀብቶች፣ ለሀገር እድገት መንሰራራት፣ለአለምአቀፍ የገበያ ትስስር፣ለዜጎች የነፍስ ወከፍ ገቢ፣ለአጠቃላይ የገበያ እድገት እንቅስቃሴ ከፍተኛ በርን የከፈተ ሲሆን እኝህን መሪዎችንና እና ተባባሪዎቻቸውን አለማመስገን ንፉግነት መሆኑ ያነበበኩት እና ለመመረቂያ ጽሁፌ ያጠናውት " The Challenges and Opportunities of the capital market proclamation implementation " ማለትም በአማረኛ ለማስገንዘብ ያህል "የካፒታል ገበያ አዋጅ አፈጻጸም ተግዳሮት እና መጻኢ እድል" በሚል በአዲስአበባ ዩኒቨርስቲ የታተመው ጹሁፍ ምስክር ይሆኑኛል።
ይሁን እንጂ የደርግ መንግስት ስልጣን ከያዘ በኋላ የሶሻሊስት ስረአት መንግስትን ባህርይ ያለው መሆኑን ተከትሎ የካፒታል ገበያ የህግ ማእቀፍ እንዳይኖረው እንዲሁም የገበያ መር ስረአትን የማይከተል በመሆኑ የካፒታል ገበያ ቦታ እንዳይኖረው አድርጎት አሁን ግን ጊዜው ደርስ የህግ ማእቀፍ እንዲኖረው ተደርጓል።
2. አሁን ላይ የካፒታል ገበያ የህግ ማእቀፍ ምን ይመስላል?
አሁን ባለንበት የኢፊድሪ ህገመንግስት ዲሞክርያሲያዊ እና ገበያ መር ስረአትን ፈቃጅ ሲሆን ይህን ተከትሎም ለሀገር እድገት የሚበጁ የንግድ ስረአታችንን የሚያዘምኑ ከአለም የገበያ ስረአት ጋር እኩል የሚሄዱ ህጎች እየወጡ የሚገኙ ሲሆን አንዱም የኢትዮጲያ ካፒታል ገበያ አዋጅ ቀጥር 1248/13 ነው።በዚህ አዋጅ አንቀጽ 3 ላይ የካፒታል ገበያ ባለስልጣን የተቋቋመ ሲሆን ይህን ተከትሎም የተለያዩ ደንብ እና መመሪያዎች በመውጣት ላይም ይገኛሉ።
ይህ ለሀገራችን እድገት እጅግ አስፈላጊ በመሆኑ ሌሎች ህጎችም ሊደግፉ እና ተጣጥመው ሊተገበሩ የሚገባ በመሆኑ የብሔራዊ ባንክ አዋጅ፣የንግድ ባንክ አዋጅ፣ የኢፊድሪ ንግድ አዋጅ ቁጥር 1243/2013 ሌሎች የፋይናንስ እና የንግድ ተቋማት ህጎች በመውጣት በመሻሻል ላይ ይገኛሉ። በካፒታል ገበያ አዋጅ ቁጥር 1248/13 ስር የሚታቀፉ ወይም የታቀፉ ዘርፈ ብዙ ተቋማት የሚገኙ ሲሆኑ ዋናው ጉዳይ ግን የሙአለ ንዋይ ሰነድ ገበያን ተፈጻሚ የሚያደርጉ ናቸው።
የሙአለ ሰነድ ገበያ በዋናነት ለመጥቀስ ያህል በአዋጁ አንቀጽ 31 መሠረት የሚመሰረት ሲሆን ይህን በተመለከተ የኢፊድሪ መንግስትም ስራ መጀመሩን አብስሯል። ይህ ዋናው የአዋጁ መቋቋም መሠረታዊ አላማ ነው። ሌላው የመወእለ ሰነዶች አስቀማጭ ክፍያ አጣሪ ፈጻሚ ኩባንያ በአዋጁ የህግ እውቅና የተሰጠው ሲሆን ይህ ግብይት የሚፈጸምባቸውን ሰነዶች ክፍያ አፈጻጸም ከእዳና ከተለያዩ ክፍያዎች ነጻ ስለመሆኑ በማጣራት ሰነዶችን በመለየት የሚያስቀምጥ ነው። በዚህ ረገድ ብሔራዊ ባንክም ስልጣን የተሰጠበት አግባብ በአዋጁ ላይ ተዘርዝሮ የተቀመጠ ነው። የመንግስት መዋአለ ሰነዶችን በተመለከተ ሰነዶችን የማስቀመጥ የማስተዳደር ስልጣን ተሰጥቶታል።
3. .ሙአለ ንዋይ ሰነዶች ምንድን ናቸው?
የሰነደ ሙዓለ ንዋይ (Securities) ማለት በገንዘብ ሊተመን የሚችል ባለቤትነትን የሚገልጽ ሰነድ ማለት ሲሆን ሊሸጥ፣ ሊለወጥ ወይም በዋስትና ሊሰጥ የሚችል መብት የሚያቋቁም ሰነድ ነው፡፡ በእኛ አገር የሚታወቁት የሰነደ ሙዓለ ንዋይ ዓይነቶች አክሲዮን፣ ቦንድና የግምጃ ቤት ሰነድ ናቸው፡፡ ባደጉት አገሮች የተለያዩ ዓይነት የሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ይገበያያሉ፡፡ እነዚህም አክሲዮኖችን (Shares)፣ የዕዳ ሰነዶችን (Debt Instruments)፣ ብድሮችን (Loans)፣ ቦንዶችንና ሌሎች ወደ ኩባንያ ካፒታልነት ሊቀየሩ የሚችሉ ስምምነቶችን ያካትታል፡፡ በተጨማሪም ሁሉም በመንግሥት ወይም በመንግሥት የልማት ድርጅቶች የወጡና
ለግብይት የሚውሉ የሕዝብ የብድር ሰነደ ሙዓለ ንዋዮችን፣ ለወደፊት የሚፈጸሙ የውል ዓይነቶችን (Futures)፣ ያለ ግዴታ የመግዛት ወይም የመሸጥ መብት ለገዥው የሚሰጡ ሰነዶችን (Options)፣ ተዛማጅን (Derivatives) እና በጋራ የኢንቨስትመንት ፈንድ ውስጥ ያለ የድርሻ ክፍልፋይ (Units in a Collective Investment Scheme) ይይዛል፡፡
እነዚህንና ሌሎች የካፒታል ገበያ ሰነዶችን በአገራችን በተማከለ ገበያ ለማገበያየት እንዲያመች እንደ ሌሎቹ አገሮች የራሱ የሆነ ሒደትን መዘርጋት፣ መደገፍ፣ መቆጣጠር ብሎም መከታተል የሚያስችል የሕግ ማዕቀፍ ማውጣት አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ የካፒታል ገበያ አዋጅ ወጥቶ ወደ ሥራ ተገብቷል፡፡ በካፒታል ገበያ አዋጅ ቁጥር 1248/13 አንቀጽ 2(62) መሠረት ሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ማለት ከላይ በሌሎች አገሮች ግብይት ይደረግባቸዋል የተባሉትን ሰነዶች ጨምሮ፣ የካፒታል ገበያ ባለሥልጣን የሰነደ ሙዓለ ንዋይ ናቸው ብሎ የሚወስናቸውን ማናቸውም በግብይት የድርሻ ባለቤትነትን የሚያረጋግጡና በባለሥልጣኑ ፈቃድ መሠረት የሚተላለፉ ሰነዶችን ይጨምራል፡፡
4. የሙአለ ሰነዶች ገበያ መመዝገብ እና መሠረዝ
ሌላው ደግሞ በዚህ መግቢያ መነሳት ያለበት ነጥብ በሙአለ ሰነዶች ገበያ የሚመዘገቡ ሰነዶች ሲሆኑ በዚህ የሚሳተፉ ተቋማት አስፈላጊውን መሥፈርት አሟልተው በጥንቃቄ ተመርምረው የሚመዘገቡ ናቸው። እነዚህም የተመዘገቡ ኩባንያዎች listing companies ሲባሉ ነገር ግን በተለያየ ምክንያት በግብይት ሂደት ውስጥ መረጃ በማሳሳት ገብተው ወይም ወንጀል ፈጽመው ወይም ግዴታቸውን ሳይወጡ ቀርተው እንደሆነ ከገበያው የሚሰረዙበት ስረአት በህጉ የተቀመጡ ሲሆን ከገበያው የተሰረዙ ኩባንያዎች/delisting campany/በመባል ይታወቃሉ። እነዚህን የካፒታል ገበያ አላማ ከዳር ለማድረስ መንግስት በራሱ ብቻ የሚከውነው ሳይሆን ለተለያዩ አገልግሎት ብቁ ለሆኑ የግል አግልግሎት ሰጪዎች ብቁ ሆነው ከተገኙ ፍቃድ በሚሰጥበት አግባብ የሚጠበቅባቸውን መስፈርት የሚያሟሉ ከሆነ ፍቃድ ተሰጥቶአቸው የሚሰሩበት አግባብ እንዳለ በአዋጁ አንቀጹ 55 ላይ በዝርዝር ተቀምጧል።
5. የኢትዮጲያ ካፒታል ገበያ አስተዳደር ፍርድ ቤት
ሌላው ትኩረት የምናደርግበት በአዋጁ አንቀጽ 64 መሠረት የተቋቋመ ሲሆን ይህም የካፒታል ገበያ አስተዳደር ፍርድ ቤት ነው። ይህ ፍርድ ቤት ሙእለ ሰነዶች ግብይት ላይ አስመልክቶ በዚህ አዋጅ ሽፋን ስር በሚወድቁ አጠቃላይ ተግባራት ላይ በባለስልጣኑ ውሳኔዎች ላይ በሚሰጡ በሚተላለፉ አስተዳደራዊ ውሳኔዎች ላይ ቅሬታ ያለው ወገን ክስ አቅርቦ የሚታይበት ሲሆን በዚህ ፍርድ ቤት የሚሰጡ ውሳኔች ላይ ቅር የተሰኘ ወገን በመሠረታዊ የህግ ስህተት ላይ ብቻ ለፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ይግባኝ የሚጠየቅበት ይሆናል። ይህ ማለት የፍሬ ነገር ክርክር ጉዳዮች በተመለከተ የክርክር ሂደት እዚሁ የካፒታል አስተዳደር ፍርድ ቤት የሚያልቅ በመሆኑ ጥንቃቄ ሊደረግ የሚገባው ነው።
በዚህ ካፒታል ገበያ አስተዳደር ፍርድ ቤት የሚሾሙ ዳኞች በጠቅላይ ሚኒስትሩ ሲሆን በዚህ ዘርፍ የተለየ በእውቀት በልምድ በስልጠና በሀገር ወጭም ጭምር የዳበሩ ልዩ እውቀትና ልምድ ያላቸው ሊሆኑ ይገባል። ይህ ካልሆነ ከፈጣን እና ፍትሀዊ አገልግሎት ከመስጠት አንጻር በቶሎ ውሳኔ የማይሰጥበት ከሆነ በዚህ ዘርፍ ለሚሳተፉ ኢንቨስተሮች፣ተቋማት ለሙአለ ሰነድ ግብይት ስራ ዘርፍ እና ኢትዮጲያ ሀገራችን ለጀመረችው የዚህ የካፒታል ገበያ እድገት ጎታች ሊሆን ስለሚችል ይህ ኢንቨስተሮችን የሚያርቅ ተስፋ የሚያስቆርጥ ይልቁንም የማይስተማምን ተገማችነትን የሚያሳጣ መሆን የለበትም ። ከዚህ አንጻር የፍርድ ቤቱ ድጋፍ ሰጪ ሰራተኞች፣በወንጀል ጉዳይ ደግሞ መርማሪዎች፣አቃቢ ህጎች በተለየ እውቀት ፣ ልምድ፣ ስልጠና የዳበሩ ሊሆኑ ያስፈልጋል። ይህም ማለት ዳኞችን በዋናነት ጨምሮ ስለ ሙአለ ንዋይ ሰነዶ ምንነት፣ባህርይ፣ግብይት፣ ህግና መመሪያዎቻቸውን በዚህ ዘርፍ የሚሳተፋትን ኩባንያ፣ኢንቨስተሮችን፣ፍቃድ የተሰጣቸውን አገልግሎት ተቋማትን በተሳታፊ ኩባንያ ውስጥ ያሉ ሰራተኞች መብትና ግዴታዎችን የካፒታል ገበያ ባለስልጣን ስልጣኑንና ተግባሩን ኀላፊነቱን ተጠያቂነቱን በዚህ ዘርፍ ስር የሚገኙ ሰራተኞችን መብት ግዴታ አሰራሮቻቸውን ማወቁ ለዚህ ለሚመለከተው ፍርድ ቤት ፍትህ አሰጣጥ እጅግ ጠቃሚ ነው።
6. ሲጠቃለል
ይህን አዋጅ ባቀፈው ህግጋት እና አላማ ልክ ተፈጻሚ ለማድረግ ያሉን መልካም አጋጣሚዎች እንደ ሀገር ምን ምን እንደሆኑ መታየቱ እጅግ በጣም አስፈላጊ ነው። የዚህን አዋጅ ተፈጻሚነት ከዳር ከማድረስ አንጻር በሚደረገው ከፍተኛ ትንቅንቅ ሊያጋጥሙ የሚችሉ ተግዳሮች ምን ምን ናቸው ለእነዚህስ መሠረታዊ የሚሆን መፍቴዎች ምንድን ናቸው በሚሉ በዝርዝር አስፈላጊ በሚባሉ ነጥቦች ላይ መሠረታዊ ትንተና ሊሰጥበት የሚገባ ሲሆን የሌሎች ሀገረች ልምድና ተሞክሮ ጭምር የመፍትሄ አካል ሆኖ መወሰዱ ወሳኝ ነገር ነው።
በአጠቃላይ የካፒታል ገበያ ህግ ለሀገራችን እጅግ ጠቃሚ ከመሆነ የተነሳ ከ19ኛ ክ/ዘመን ወዲህ ጀምሮ ባለተማከለ የገበያ አሰራር የሙአለ ሰነድ ሽያጮች ይከናወኑ እንደነበሩ እና በዚህ ለሀገራችን እድገት ወሰኝ የነበረ ሲሆን ይህንና አለምአቀፍ ልምዶች ህጎች ትስስሮች በመረዳት በተማከለ የካፒታል ገበያ ስረአት ውስጥ በመጓዝ ሀገርን እና ዜጎችን በኢኮኖሚ እድገት ከፍ ለማድረግ የካፒታል ገበያ አዋጅ ቁጥር 1248/13 ይህንንም ተከትሎ ሌሎች ሊያሰሩ የሚችሉ ደንቦችን መመሪያዎችን በማውጣት ላይ የሚገኝ ሲሆን ከዚህ በፊት የነበሩ የንግድ የባንክ፣የፋይናንስ ህጎች በመሻሻል ላይ ይገኛሉ።
መንግስትም ይህን የሚመጥን በህግ ማእቀፉ እንደተቀመጠው በቴክኖሎጂ የታገዙ ተቋማትን መገንባት የሚገባ ሲሆን ከዚህ ውስጥ የሰው ሀይል ማብቃትም በተመለከተ ትኩረት ሊወሰድበት የሚገባው ነው። ማህበረሰቡ ኢንቨስተሩ ኩባንያውም በዚህ ልክ እንዲነቃቃ አስፈላጊውን ግንዛቤ ሊሰጠው ያስፈልጋል። የካፒታል ገበያ ባለስልጣኑም በአዋጁ የተሰጠውን ትልቅ ኀላፊነት ለመወጣት አስፈላጊውን ዝግጅት ሊወስድ የሚገባ ሲሆን በግብይት ሂደት ተሳታፊ የሆኑ ቅን ባለሀብቶችን መብት ጥበቃ ሊያደርግ የሚያስፈልግ ሲሆን አጭበርባሪዎችን ለአሰራር እንቅፋት የሚፈጥሩትን በመለየት እንዲታረሙ ከማድረግ አንጻር ተገቢውን ጥረት ሊያደርግ የሚገባው ነው። ይህ ሲሆን የካፒታል ገበያ አዋጅ 1248/13 ተፈጻሚ በማድረግ ለሀገራችን ትልቅ የኢኮኖሚ ፋይዳ ያለው ስለመሆኑ አያጠያይቅም።
ማጣቀሻዎች/References/
1. የኢፊድሪ ህገመንግስት አዋጅ ቁጥር 1/1987
2. የካፒታል ገበያ አዋጅ ቁጥር 1248/13
3. Fantahun Delelew, Challenge and opportunities of the implementation of capital proclamation 1248/13,Addisababa University
(የካፒታል አዋጁ አፈጻጸም ተግዳሮት እና መጻኢ እድል)
4. የብሔራዊ ባንክ አዋጅ ቁጥር 1359/17
5. ስለ ባንክ ስራዎች አዋጅ ቁጥር 1360/17
https://www.facebook.com
https://t.me/Fantahunlawye...
በኢትዮጵያ ህግ ማእቀፍ
የኢትዮጲያ ካፒታል አዋጅ ቁጥር 1248/13
ጠበቃና የህግ አማካሪ ፋንታሁን ደለለው
መግቢያ #ethiopia | የካፒታል ገበያ በኢትዮጵያ በህግ ማእቀፍ ተደግፎ የመዋለ ሰነዶችን ሽያጭ በማሳደግ ረገድ ሀገራችን የካፒታል አዋጅ ቁጥር 1248/13 አውጥቶ በስራ ላይ መዋሉ የእነዚህ ሰነዶችን ሽያጭ ገበያ በመፍጠር ኢንቨስተሮችን ከመሳብ ፣ የንግድ ማህበራትን፣ባንኮችን ከማሳደግ፣ የሀገሪቱን የኢኮኖሚ እድገት ከፍ ከማድረግ አንጻር ዘርፈ ብዙ የተሳለጠ የንግድ ትስስር የሚፈጥር ሲሆን በዚህ ጽሁፍ ከህግ ጋር ተያይዞ ያለውን ይዘት ለማህበረሰቡ ግንዛቤ ለመስጠት ይህን ጽሁፍ ወደ እናንተ አቅርበናል።
1. የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ታሪካዊ ዳራ
ኢትዮጵያ ብዙ የህግ ታሪክ ስለ ካፒታል ገበያ እንደሌሎች ሀገራት እንደሌላት የተለያዩ ስለካፒታል ገበያ የተመለከቱ የኢትዮጵያን ታሪክ መመልከት የሚቻል ነው። የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ታሪካዊ ዳራን ስናጤን በአጼ ዘመነ መንግስት እ.ኤ.አ በ1867 ዓ.ም በአጼ ሚኒሊክ ዘመነ መንግስት የኢትዮ ጅቡቲን ሀዲድ ለመዘርጋት የ40 ሚሊዮን ፍራንክ አክስዮን በፈረንሳይ ሀገር መሸጣቸው ታሪክ ያወሳል።በእሳቸው ዘመን የተቋቋመው የመጀመርያው ባንክ፣ አቢሲኒያ ባንክ ሲመሠረት አክሲዮኖቹ ከአዲስ አበባ በተጨማሪ ኒውዮርክ፣ ፓሪስ፣ ለንደንና ቪየና እንደተሸጡ የታሪክ ድርሳናት ያስረዳሉ፡፡
እ.ኤ.አ. በ1956 የኢትዮጵያ የቄራዎች ድርጅት ለሕዝብ ሽያጭ የወጣ ሲሆን፣ እሱን ተከትሎ እ.ኤ.አ. ከ1957 እስከ 1963 ባለው ጊዜ ውስጥ የኢትዮጵያ ጠርሙስ ፋብሪካ (Ethiopian Bottling Company)፣ ኢንዶ-ኢትዮጵያን ጨርቃ ጨርቅ፣ ኤችቪኤ ኢትዮጵያ፣ ሳባ ጠጅ፣ ተንዳሆ ተክልና የአዲስ አበባ ባንክ ለሕዝብ ሽያጭ መውጣታቸውን ለማወቅ ተችሏል፡፡ በተጨማሪ እ.ኤ.አ. በ1959 ወንጂ ስኳር ፋብሪካ ለሕዝብ ሽያጭ የቀረበ ድርጅት መሆኑንና በወቅቱ በሦስት ወራት ውስጥ ከአክሲዮን ሽያጭ 2.5 ሚሊዮን ዶላር መሰብሰብ የተቻለ ሲሆን፣ ኤችቪኤ የተባለው የሆላንድ ኩባንያ አብዛኛውን አክሲዮን መግዛቱ ይነገራል፡፡ እንዲሁም ሕዝቡም ቀላል ሊባል በማይችል መልኩ በግብይት መሳተፉንና ድርሻ መግዛቱን ጄዲቮን ፒስኬ የተባለ ጸሐፊ፣ «አክሲዮንና የአክሲዮን ግብይት በአዲስ አበባ» በሚለው መጽሐፉ ከትቦት ይገኛል።
በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዘመነ መንግሥት በ1960 ዓ.ም. በኢትዮጵያ መንግሥት ባንክ (State Bank of Ethiopia) ውስጥ የአክሲዮን ግብይት መምርያ መቋቋሙ የአክሲዮን ግብይቱን ለማሳደግ ከፍተኛ ሚና ተጫውቷል፡፡ ይህንን መምርያ ማደራጀት የአክሲዮን ገበያን ለማስፋፋት በመንግሥት የተወሰደ የመጀመርያው ተቋማዊ አደረጃጀት ዕርምጃ እንደሆነ ይነገራል፡፡ በወቅቱ የተለያዩ ኢንቨስተሮችን በግብይት በማሳተፍና ዋጋ እንዲሰጡ በማድረግ፣ እንዲሁም በተለያዩ መንገዶች ዋጋ እንዲወሰን ይደረግ ነበር፡፡
እ.ኤ.አ. በ1965 የአክሲዮን ግብይት እያደገ በመሄዱ፣ የሕዝብን እምነት በማግኘቱ፣ ኢኮኖሚውም ዕድገት በማሳየቱ፣ አዳዲስ ኀይለስላሴ ዘመነመንግስት የካፒታል ገበያ የህግ ማእቀፍ ኖሮት የተለያዩ አስፈጻሚ ተቋሟት የማቋቋም የማደራጀት እና የመነቃቃት ስራዎች ተሞክረዋል። ታላቁ የህዳሴ ግድብ ለመገንባት በተደረገው ህዝባዊ ንቅናቄም ብዙ የቦንድ ሽያጭ ለዜጎች፣ ሀገር በቀል ድርጅቶች ፣ ለትውልደ ኢትዮጲያን ፣ ዲያስፖራ ለሌሎችም ተሳታፊ አካላት ተሽጦ በብዙ ቢሊዮን ብር ተሰብስቦ ታላቁን ህዳሴ ግድብ ተገንብቷል።
ይህ ህጉ ከመውጣቱ በፊት ባልተማከለ አሰራር የተፈጸመ ቢሆንም የካፒታል ገበያ ስረአት እጅግ አስፈላጊ መሆኑን ያሳያል። ከዚህም ባለፈ የገበያ መር ስረአት የሚደግፍ ሲሆን ለነጋዴዎች፣ለባለሀብቶች፣ ለሀገር እድገት መንሰራራት፣ለአለምአቀፍ የገበያ ትስስር፣ለዜጎች የነፍስ ወከፍ ገቢ፣ለአጠቃላይ የገበያ እድገት እንቅስቃሴ ከፍተኛ በርን የከፈተ ሲሆን እኝህን መሪዎችንና እና ተባባሪዎቻቸውን አለማመስገን ንፉግነት መሆኑ ያነበበኩት እና ለመመረቂያ ጽሁፌ ያጠናውት " The Challenges and Opportunities of the capital market proclamation implementation " ማለትም በአማረኛ ለማስገንዘብ ያህል "የካፒታል ገበያ አዋጅ አፈጻጸም ተግዳሮት እና መጻኢ እድል" በሚል በአዲስአበባ ዩኒቨርስቲ የታተመው ጹሁፍ ምስክር ይሆኑኛል።
ይሁን እንጂ የደርግ መንግስት ስልጣን ከያዘ በኋላ የሶሻሊስት ስረአት መንግስትን ባህርይ ያለው መሆኑን ተከትሎ የካፒታል ገበያ የህግ ማእቀፍ እንዳይኖረው እንዲሁም የገበያ መር ስረአትን የማይከተል በመሆኑ የካፒታል ገበያ ቦታ እንዳይኖረው አድርጎት አሁን ግን ጊዜው ደርስ የህግ ማእቀፍ እንዲኖረው ተደርጓል።
2. አሁን ላይ የካፒታል ገበያ የህግ ማእቀፍ ምን ይመስላል?
አሁን ባለንበት የኢፊድሪ ህገመንግስት ዲሞክርያሲያዊ እና ገበያ መር ስረአትን ፈቃጅ ሲሆን ይህን ተከትሎም ለሀገር እድገት የሚበጁ የንግድ ስረአታችንን የሚያዘምኑ ከአለም የገበያ ስረአት ጋር እኩል የሚሄዱ ህጎች እየወጡ የሚገኙ ሲሆን አንዱም የኢትዮጲያ ካፒታል ገበያ አዋጅ ቀጥር 1248/13 ነው።በዚህ አዋጅ አንቀጽ 3 ላይ የካፒታል ገበያ ባለስልጣን የተቋቋመ ሲሆን ይህን ተከትሎም የተለያዩ ደንብ እና መመሪያዎች በመውጣት ላይም ይገኛሉ።
ይህ ለሀገራችን እድገት እጅግ አስፈላጊ በመሆኑ ሌሎች ህጎችም ሊደግፉ እና ተጣጥመው ሊተገበሩ የሚገባ በመሆኑ የብሔራዊ ባንክ አዋጅ፣የንግድ ባንክ አዋጅ፣ የኢፊድሪ ንግድ አዋጅ ቁጥር 1243/2013 ሌሎች የፋይናንስ እና የንግድ ተቋማት ህጎች በመውጣት በመሻሻል ላይ ይገኛሉ። በካፒታል ገበያ አዋጅ ቁጥር 1248/13 ስር የሚታቀፉ ወይም የታቀፉ ዘርፈ ብዙ ተቋማት የሚገኙ ሲሆኑ ዋናው ጉዳይ ግን የሙአለ ንዋይ ሰነድ ገበያን ተፈጻሚ የሚያደርጉ ናቸው።
የሙአለ ሰነድ ገበያ በዋናነት ለመጥቀስ ያህል በአዋጁ አንቀጽ 31 መሠረት የሚመሰረት ሲሆን ይህን በተመለከተ የኢፊድሪ መንግስትም ስራ መጀመሩን አብስሯል። ይህ ዋናው የአዋጁ መቋቋም መሠረታዊ አላማ ነው። ሌላው የመወእለ ሰነዶች አስቀማጭ ክፍያ አጣሪ ፈጻሚ ኩባንያ በአዋጁ የህግ እውቅና የተሰጠው ሲሆን ይህ ግብይት የሚፈጸምባቸውን ሰነዶች ክፍያ አፈጻጸም ከእዳና ከተለያዩ ክፍያዎች ነጻ ስለመሆኑ በማጣራት ሰነዶችን በመለየት የሚያስቀምጥ ነው። በዚህ ረገድ ብሔራዊ ባንክም ስልጣን የተሰጠበት አግባብ በአዋጁ ላይ ተዘርዝሮ የተቀመጠ ነው። የመንግስት መዋአለ ሰነዶችን በተመለከተ ሰነዶችን የማስቀመጥ የማስተዳደር ስልጣን ተሰጥቶታል።
3. .ሙአለ ንዋይ ሰነዶች ምንድን ናቸው?
የሰነደ ሙዓለ ንዋይ (Securities) ማለት በገንዘብ ሊተመን የሚችል ባለቤትነትን የሚገልጽ ሰነድ ማለት ሲሆን ሊሸጥ፣ ሊለወጥ ወይም በዋስትና ሊሰጥ የሚችል መብት የሚያቋቁም ሰነድ ነው፡፡ በእኛ አገር የሚታወቁት የሰነደ ሙዓለ ንዋይ ዓይነቶች አክሲዮን፣ ቦንድና የግምጃ ቤት ሰነድ ናቸው፡፡ ባደጉት አገሮች የተለያዩ ዓይነት የሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ይገበያያሉ፡፡ እነዚህም አክሲዮኖችን (Shares)፣ የዕዳ ሰነዶችን (Debt Instruments)፣ ብድሮችን (Loans)፣ ቦንዶችንና ሌሎች ወደ ኩባንያ ካፒታልነት ሊቀየሩ የሚችሉ ስምምነቶችን ያካትታል፡፡ በተጨማሪም ሁሉም በመንግሥት ወይም በመንግሥት የልማት ድርጅቶች የወጡና
ለግብይት የሚውሉ የሕዝብ የብድር ሰነደ ሙዓለ ንዋዮችን፣ ለወደፊት የሚፈጸሙ የውል ዓይነቶችን (Futures)፣ ያለ ግዴታ የመግዛት ወይም የመሸጥ መብት ለገዥው የሚሰጡ ሰነዶችን (Options)፣ ተዛማጅን (Derivatives) እና በጋራ የኢንቨስትመንት ፈንድ ውስጥ ያለ የድርሻ ክፍልፋይ (Units in a Collective Investment Scheme) ይይዛል፡፡
እነዚህንና ሌሎች የካፒታል ገበያ ሰነዶችን በአገራችን በተማከለ ገበያ ለማገበያየት እንዲያመች እንደ ሌሎቹ አገሮች የራሱ የሆነ ሒደትን መዘርጋት፣ መደገፍ፣ መቆጣጠር ብሎም መከታተል የሚያስችል የሕግ ማዕቀፍ ማውጣት አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ የካፒታል ገበያ አዋጅ ወጥቶ ወደ ሥራ ተገብቷል፡፡ በካፒታል ገበያ አዋጅ ቁጥር 1248/13 አንቀጽ 2(62) መሠረት ሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ማለት ከላይ በሌሎች አገሮች ግብይት ይደረግባቸዋል የተባሉትን ሰነዶች ጨምሮ፣ የካፒታል ገበያ ባለሥልጣን የሰነደ ሙዓለ ንዋይ ናቸው ብሎ የሚወስናቸውን ማናቸውም በግብይት የድርሻ ባለቤትነትን የሚያረጋግጡና በባለሥልጣኑ ፈቃድ መሠረት የሚተላለፉ ሰነዶችን ይጨምራል፡፡
4. የሙአለ ሰነዶች ገበያ መመዝገብ እና መሠረዝ
ሌላው ደግሞ በዚህ መግቢያ መነሳት ያለበት ነጥብ በሙአለ ሰነዶች ገበያ የሚመዘገቡ ሰነዶች ሲሆኑ በዚህ የሚሳተፉ ተቋማት አስፈላጊውን መሥፈርት አሟልተው በጥንቃቄ ተመርምረው የሚመዘገቡ ናቸው። እነዚህም የተመዘገቡ ኩባንያዎች listing companies ሲባሉ ነገር ግን በተለያየ ምክንያት በግብይት ሂደት ውስጥ መረጃ በማሳሳት ገብተው ወይም ወንጀል ፈጽመው ወይም ግዴታቸውን ሳይወጡ ቀርተው እንደሆነ ከገበያው የሚሰረዙበት ስረአት በህጉ የተቀመጡ ሲሆን ከገበያው የተሰረዙ ኩባንያዎች/delisting campany/በመባል ይታወቃሉ። እነዚህን የካፒታል ገበያ አላማ ከዳር ለማድረስ መንግስት በራሱ ብቻ የሚከውነው ሳይሆን ለተለያዩ አገልግሎት ብቁ ለሆኑ የግል አግልግሎት ሰጪዎች ብቁ ሆነው ከተገኙ ፍቃድ በሚሰጥበት አግባብ የሚጠበቅባቸውን መስፈርት የሚያሟሉ ከሆነ ፍቃድ ተሰጥቶአቸው የሚሰሩበት አግባብ እንዳለ በአዋጁ አንቀጹ 55 ላይ በዝርዝር ተቀምጧል።
5. የኢትዮጲያ ካፒታል ገበያ አስተዳደር ፍርድ ቤት
ሌላው ትኩረት የምናደርግበት በአዋጁ አንቀጽ 64 መሠረት የተቋቋመ ሲሆን ይህም የካፒታል ገበያ አስተዳደር ፍርድ ቤት ነው። ይህ ፍርድ ቤት ሙእለ ሰነዶች ግብይት ላይ አስመልክቶ በዚህ አዋጅ ሽፋን ስር በሚወድቁ አጠቃላይ ተግባራት ላይ በባለስልጣኑ ውሳኔዎች ላይ በሚሰጡ በሚተላለፉ አስተዳደራዊ ውሳኔዎች ላይ ቅሬታ ያለው ወገን ክስ አቅርቦ የሚታይበት ሲሆን በዚህ ፍርድ ቤት የሚሰጡ ውሳኔች ላይ ቅር የተሰኘ ወገን በመሠረታዊ የህግ ስህተት ላይ ብቻ ለፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ይግባኝ የሚጠየቅበት ይሆናል። ይህ ማለት የፍሬ ነገር ክርክር ጉዳዮች በተመለከተ የክርክር ሂደት እዚሁ የካፒታል አስተዳደር ፍርድ ቤት የሚያልቅ በመሆኑ ጥንቃቄ ሊደረግ የሚገባው ነው።
በዚህ ካፒታል ገበያ አስተዳደር ፍርድ ቤት የሚሾሙ ዳኞች በጠቅላይ ሚኒስትሩ ሲሆን በዚህ ዘርፍ የተለየ በእውቀት በልምድ በስልጠና በሀገር ወጭም ጭምር የዳበሩ ልዩ እውቀትና ልምድ ያላቸው ሊሆኑ ይገባል። ይህ ካልሆነ ከፈጣን እና ፍትሀዊ አገልግሎት ከመስጠት አንጻር በቶሎ ውሳኔ የማይሰጥበት ከሆነ በዚህ ዘርፍ ለሚሳተፉ ኢንቨስተሮች፣ተቋማት ለሙአለ ሰነድ ግብይት ስራ ዘርፍ እና ኢትዮጲያ ሀገራችን ለጀመረችው የዚህ የካፒታል ገበያ እድገት ጎታች ሊሆን ስለሚችል ይህ ኢንቨስተሮችን የሚያርቅ ተስፋ የሚያስቆርጥ ይልቁንም የማይስተማምን ተገማችነትን የሚያሳጣ መሆን የለበትም ። ከዚህ አንጻር የፍርድ ቤቱ ድጋፍ ሰጪ ሰራተኞች፣በወንጀል ጉዳይ ደግሞ መርማሪዎች፣አቃቢ ህጎች በተለየ እውቀት ፣ ልምድ፣ ስልጠና የዳበሩ ሊሆኑ ያስፈልጋል። ይህም ማለት ዳኞችን በዋናነት ጨምሮ ስለ ሙአለ ንዋይ ሰነዶ ምንነት፣ባህርይ፣ግብይት፣ ህግና መመሪያዎቻቸውን በዚህ ዘርፍ የሚሳተፋትን ኩባንያ፣ኢንቨስተሮችን፣ፍቃድ የተሰጣቸውን አገልግሎት ተቋማትን በተሳታፊ ኩባንያ ውስጥ ያሉ ሰራተኞች መብትና ግዴታዎችን የካፒታል ገበያ ባለስልጣን ስልጣኑንና ተግባሩን ኀላፊነቱን ተጠያቂነቱን በዚህ ዘርፍ ስር የሚገኙ ሰራተኞችን መብት ግዴታ አሰራሮቻቸውን ማወቁ ለዚህ ለሚመለከተው ፍርድ ቤት ፍትህ አሰጣጥ እጅግ ጠቃሚ ነው።
6. ሲጠቃለል
ይህን አዋጅ ባቀፈው ህግጋት እና አላማ ልክ ተፈጻሚ ለማድረግ ያሉን መልካም አጋጣሚዎች እንደ ሀገር ምን ምን እንደሆኑ መታየቱ እጅግ በጣም አስፈላጊ ነው። የዚህን አዋጅ ተፈጻሚነት ከዳር ከማድረስ አንጻር በሚደረገው ከፍተኛ ትንቅንቅ ሊያጋጥሙ የሚችሉ ተግዳሮች ምን ምን ናቸው ለእነዚህስ መሠረታዊ የሚሆን መፍቴዎች ምንድን ናቸው በሚሉ በዝርዝር አስፈላጊ በሚባሉ ነጥቦች ላይ መሠረታዊ ትንተና ሊሰጥበት የሚገባ ሲሆን የሌሎች ሀገረች ልምድና ተሞክሮ ጭምር የመፍትሄ አካል ሆኖ መወሰዱ ወሳኝ ነገር ነው።
በአጠቃላይ የካፒታል ገበያ ህግ ለሀገራችን እጅግ ጠቃሚ ከመሆነ የተነሳ ከ19ኛ ክ/ዘመን ወዲህ ጀምሮ ባለተማከለ የገበያ አሰራር የሙአለ ሰነድ ሽያጮች ይከናወኑ እንደነበሩ እና በዚህ ለሀገራችን እድገት ወሰኝ የነበረ ሲሆን ይህንና አለምአቀፍ ልምዶች ህጎች ትስስሮች በመረዳት በተማከለ የካፒታል ገበያ ስረአት ውስጥ በመጓዝ ሀገርን እና ዜጎችን በኢኮኖሚ እድገት ከፍ ለማድረግ የካፒታል ገበያ አዋጅ ቁጥር 1248/13 ይህንንም ተከትሎ ሌሎች ሊያሰሩ የሚችሉ ደንቦችን መመሪያዎችን በማውጣት ላይ የሚገኝ ሲሆን ከዚህ በፊት የነበሩ የንግድ የባንክ፣የፋይናንስ ህጎች በመሻሻል ላይ ይገኛሉ።
መንግስትም ይህን የሚመጥን በህግ ማእቀፉ እንደተቀመጠው በቴክኖሎጂ የታገዙ ተቋማትን መገንባት የሚገባ ሲሆን ከዚህ ውስጥ የሰው ሀይል ማብቃትም በተመለከተ ትኩረት ሊወሰድበት የሚገባው ነው። ማህበረሰቡ ኢንቨስተሩ ኩባንያውም በዚህ ልክ እንዲነቃቃ አስፈላጊውን ግንዛቤ ሊሰጠው ያስፈልጋል። የካፒታል ገበያ ባለስልጣኑም በአዋጁ የተሰጠውን ትልቅ ኀላፊነት ለመወጣት አስፈላጊውን ዝግጅት ሊወስድ የሚገባ ሲሆን በግብይት ሂደት ተሳታፊ የሆኑ ቅን ባለሀብቶችን መብት ጥበቃ ሊያደርግ የሚያስፈልግ ሲሆን አጭበርባሪዎችን ለአሰራር እንቅፋት የሚፈጥሩትን በመለየት እንዲታረሙ ከማድረግ አንጻር ተገቢውን ጥረት ሊያደርግ የሚገባው ነው። ይህ ሲሆን የካፒታል ገበያ አዋጅ 1248/13 ተፈጻሚ በማድረግ ለሀገራችን ትልቅ የኢኮኖሚ ፋይዳ ያለው ስለመሆኑ አያጠያይቅም።
ማጣቀሻዎች/References/
1. የኢፊድሪ ህገመንግስት አዋጅ ቁጥር 1/1987
2. የካፒታል ገበያ አዋጅ ቁጥር 1248/13
3. Fantahun Delelew, Challenge and opportunities of the implementation of capital proclamation 1248/13,Addisababa University
(የካፒታል አዋጁ አፈጻጸም ተግዳሮት እና መጻኢ እድል)
4. የብሔራዊ ባንክ አዋጅ ቁጥር 1359/17
5. ስለ ባንክ ስራዎች አዋጅ ቁጥር 1360/17
https://www.facebook.com
https://t.me/Fantahunlawye...
4 months ago
ድሬ ማይክሮ ፋይናንስ በአዲስ አበባ የመጀመሪያውን ቅርንጫፉን በይፋ አስመረቀ
#ethiopia | በምስራቅ ኢትዮጵያ በፋይናንስ ተደራሽነት ላይ ከፍተኛ አሻራ በማሳረፍ የሚታወቀው ድሬ ማይክሮ ፋይናንስ፣ አገልግሎቱን ወደ መዲናዋ አዲስ አበባ በማስፋት የመጀመሪያ የሆነውን የቦሌ ሚካኤል ቅርንጫፍ በዛሬው ዕለት በደማቅ ስነ-ስርዓት አስመረቀ።
ተቋሙ አዲስ አበባን ጨምሮ በድሬዳዋ፣ በሐረር፣ በጅግጅጋ እና በሀሮማያ ከተሞች ተደራሽነቱን በማስፋት፣ ለህብረተሰቡ የፋይናንስ አገልግሎትን በእኩልነት ለማዳረስ እየሰራ መሆኑ በምረቃው ላይ ተገልጿል።
በተለይም በትልልቅ የፋይናንስ ተቋማት አገልግሎት ማግኘት ለሚቸገሩ እና ዝቅተኛ ገቢ ላላቸው የማኅበረሰብ ክፍሎች ተመጣጣኝ የብድርና ቁጠባ አገልግሎት መስጠትን ዋነኛ ተልዕኮው አድርጎ እየተንቀሳቀሰ ይገኛል።
በምረቃው ስነ-ስርዓት ላይ እንደተገለጸው፣ ድሬ ማይክሮ ፋይናንስ በአሁኑ ወቅት አስደናቂ የፋይናንስ አፈጻጸም እያስመዘገበ ነው ተብሏል።
በምረቃውም ስነ ስርዓት ላይ
* ከ1.7 ቢሊየን ብር በላይ የብድር ክምችት
(Total Loan Outstanding) እንዳለው፣
* ከ111 ሺህ በላይ የቁጠባና የብድር ደንበኞችን ማፍራቱን፣
* የተቋሙ አጠቃላይ ካፒታል ከ677 ሚሊየን ብር በላይ መድረሱ ተመላክቷል።
በተለይም በፋይናንስ ተቋማት ውስጥ እንደ ትልቅ ስጋት የሚታየው ለአደጋ የተጋለጠ ብድር (PAR) መጠንን ወደ 0.73% ዝቅ ማድረግ መቻሉ፣ የተቋሙን አስተማማኝነት እና የብድር አሰጣጥ ጥራት የሚያሳይ እንደሆነ ተብራርቷል።
ድሬ ማይክሮ ፋይናንስ ከመደበኛ የብድር እና ቁጠባ አገልግሎት በተጨማሪ፤ የህብረተሰቡን እሴት ያገናዘበ ከወለድ ነፃ የፋይናንስ አገልግሎት፣ የማሽነሪ ሊዝ፣ እንዲሁም እንደ ንጹህ ኢነርጂ (Clean Energy) እና ውሃና ሳኒቴሽን (WASH) ላሉ ዘርፎች የብድር አገልግሎት በመስጠት በፈጠራ ታግዞ እየሰራ እንደሚገኝ ተገልጿል።
አዲሱ የአዲስ አበባ ቅርንጫፍም ፣ ለወጣቶች፣ ለሴቶች እና ለአነስተኛ የንግድ ስራ ፈጣሪዎች የስኬት በር እንደሚሆን በምረቃው ላይ መልዕክት ተላልፏል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #diremicrofinance #financialinclusion #newbranch #addisababa #bolemichael #ethiopia #microfinance #economicempowerment #ድሬማይክሮፋይናንስ #ፋይናንስ #አዲስአበባ
#ethiopia | በምስራቅ ኢትዮጵያ በፋይናንስ ተደራሽነት ላይ ከፍተኛ አሻራ በማሳረፍ የሚታወቀው ድሬ ማይክሮ ፋይናንስ፣ አገልግሎቱን ወደ መዲናዋ አዲስ አበባ በማስፋት የመጀመሪያ የሆነውን የቦሌ ሚካኤል ቅርንጫፍ በዛሬው ዕለት በደማቅ ስነ-ስርዓት አስመረቀ።
ተቋሙ አዲስ አበባን ጨምሮ በድሬዳዋ፣ በሐረር፣ በጅግጅጋ እና በሀሮማያ ከተሞች ተደራሽነቱን በማስፋት፣ ለህብረተሰቡ የፋይናንስ አገልግሎትን በእኩልነት ለማዳረስ እየሰራ መሆኑ በምረቃው ላይ ተገልጿል።
በተለይም በትልልቅ የፋይናንስ ተቋማት አገልግሎት ማግኘት ለሚቸገሩ እና ዝቅተኛ ገቢ ላላቸው የማኅበረሰብ ክፍሎች ተመጣጣኝ የብድርና ቁጠባ አገልግሎት መስጠትን ዋነኛ ተልዕኮው አድርጎ እየተንቀሳቀሰ ይገኛል።
በምረቃው ስነ-ስርዓት ላይ እንደተገለጸው፣ ድሬ ማይክሮ ፋይናንስ በአሁኑ ወቅት አስደናቂ የፋይናንስ አፈጻጸም እያስመዘገበ ነው ተብሏል።
በምረቃውም ስነ ስርዓት ላይ
* ከ1.7 ቢሊየን ብር በላይ የብድር ክምችት
(Total Loan Outstanding) እንዳለው፣
* ከ111 ሺህ በላይ የቁጠባና የብድር ደንበኞችን ማፍራቱን፣
* የተቋሙ አጠቃላይ ካፒታል ከ677 ሚሊየን ብር በላይ መድረሱ ተመላክቷል።
በተለይም በፋይናንስ ተቋማት ውስጥ እንደ ትልቅ ስጋት የሚታየው ለአደጋ የተጋለጠ ብድር (PAR) መጠንን ወደ 0.73% ዝቅ ማድረግ መቻሉ፣ የተቋሙን አስተማማኝነት እና የብድር አሰጣጥ ጥራት የሚያሳይ እንደሆነ ተብራርቷል።
ድሬ ማይክሮ ፋይናንስ ከመደበኛ የብድር እና ቁጠባ አገልግሎት በተጨማሪ፤ የህብረተሰቡን እሴት ያገናዘበ ከወለድ ነፃ የፋይናንስ አገልግሎት፣ የማሽነሪ ሊዝ፣ እንዲሁም እንደ ንጹህ ኢነርጂ (Clean Energy) እና ውሃና ሳኒቴሽን (WASH) ላሉ ዘርፎች የብድር አገልግሎት በመስጠት በፈጠራ ታግዞ እየሰራ እንደሚገኝ ተገልጿል።
አዲሱ የአዲስ አበባ ቅርንጫፍም ፣ ለወጣቶች፣ ለሴቶች እና ለአነስተኛ የንግድ ስራ ፈጣሪዎች የስኬት በር እንደሚሆን በምረቃው ላይ መልዕክት ተላልፏል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #diremicrofinance #financialinclusion #newbranch #addisababa #bolemichael #ethiopia #microfinance #economicempowerment #ድሬማይክሮፋይናንስ #ፋይናንስ #አዲስአበባ
4 months ago
ድሬ ማይክሮፋይናንስ በአዲስ አበባ በቦሌ ሚካኤል ቅርንጫፉን አስመረቀ!
#fastmereja : ድሬ ማይክሮፋይናንስ የብድር እና ቁጠባ ተቋም በዛሬዉ እለት በአዲስ አበባ በቦሌ ሚካኤል ቅርንጫፉን በይፋ አስመርቋል።
ድሬ ማይክሮ ፋይናንስ ተቋም በድሬዳዋ አስተዳደር በከተማና በገጠር ፤ በሐረር ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት በሐረር ከተማ ፣ጅግጅጋ እና ሐሮማያ ከተሞች ቅርንጫፎችን በመክፈት ውጤታማ ሥራ እየሰራ ሲሆን ፤ በአሁኑ ሰዓት ደግሞ ተደራሽነቱን እና አገልግሎቱን ለማስፋት በአዲስ አበባ ከተማ በቦሌ ሚካኤል አካባቢ ቅርንጫፉን አስመርቋል።
ድሬ ማይክሮ ፈይናንስ ተቋም የሚሰጣቸው የብድር እና የቁጠባ አማራጮች የመደበኛ የብድርና ቁጠባ አገልግሎት፣የካፒታል ዕቃ ፋይናንስ (Machinery Lease) የወለድ አልባ የብድርና ቁጠባ አገልግሎት እና ዲጅታል የቁጠባና ብድር አገልግሎቶች እንደሆኑ ተገልጿል።
ተቋሙ ራዕይዉን ተከትሎ በትጋትና በቁርጠኝነት በሰራቸው ስራዎች አሁን ላይ የብድር ደንበኞች ላይ ያለው ጠቅላላ የብድር መጠን (Total Loan Outstanding) ከ1.7 ቢሊየን ብር በላይ ማድረስ መቻሉን ገልጿል፡፡
ከ111ሺ በላይ የብድርና ቁጠባ ደንበኞችን ማፍራት የቻለዉ ይህ ተቋም እስከ ዲሴምበር 31/2025 ላለመመለስ በአደጋ ላይ ያለውን ብድር/PAR/ ዐ.73% ማድረስ የቻለ ሲሆን የተቋሙን ካፒታል ከ677 ሚሊየን ብር በላይ ማድረስም ተችሏል፡፡
#fastmereja : ድሬ ማይክሮፋይናንስ የብድር እና ቁጠባ ተቋም በዛሬዉ እለት በአዲስ አበባ በቦሌ ሚካኤል ቅርንጫፉን በይፋ አስመርቋል።
ድሬ ማይክሮ ፋይናንስ ተቋም በድሬዳዋ አስተዳደር በከተማና በገጠር ፤ በሐረር ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት በሐረር ከተማ ፣ጅግጅጋ እና ሐሮማያ ከተሞች ቅርንጫፎችን በመክፈት ውጤታማ ሥራ እየሰራ ሲሆን ፤ በአሁኑ ሰዓት ደግሞ ተደራሽነቱን እና አገልግሎቱን ለማስፋት በአዲስ አበባ ከተማ በቦሌ ሚካኤል አካባቢ ቅርንጫፉን አስመርቋል።
ድሬ ማይክሮ ፈይናንስ ተቋም የሚሰጣቸው የብድር እና የቁጠባ አማራጮች የመደበኛ የብድርና ቁጠባ አገልግሎት፣የካፒታል ዕቃ ፋይናንስ (Machinery Lease) የወለድ አልባ የብድርና ቁጠባ አገልግሎት እና ዲጅታል የቁጠባና ብድር አገልግሎቶች እንደሆኑ ተገልጿል።
ተቋሙ ራዕይዉን ተከትሎ በትጋትና በቁርጠኝነት በሰራቸው ስራዎች አሁን ላይ የብድር ደንበኞች ላይ ያለው ጠቅላላ የብድር መጠን (Total Loan Outstanding) ከ1.7 ቢሊየን ብር በላይ ማድረስ መቻሉን ገልጿል፡፡
ከ111ሺ በላይ የብድርና ቁጠባ ደንበኞችን ማፍራት የቻለዉ ይህ ተቋም እስከ ዲሴምበር 31/2025 ላለመመለስ በአደጋ ላይ ያለውን ብድር/PAR/ ዐ.73% ማድረስ የቻለ ሲሆን የተቋሙን ካፒታል ከ677 ሚሊየን ብር በላይ ማድረስም ተችሏል፡፡
4 months ago
🏦 የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከ91% በላይ ብድሩን ለግሉ ዘርፍ መስጠቱን አስታወቀ
#ethiopia | "በግማሽ ዓመት 293.9 ቢሊዮን ብር ለግል ባለሀብቶች እና ድርጅቶች ቀርቧል"
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በተጠናቀቀው ግማሽ የበጀት ዓመት ያቀረበው የብድር መጠን ለግሉ ዘርፍ (Private Sector) ትልቅ ትኩረት የሰጠ መሆኑን ገለጸ።
ቁልፍ የብድር መረጃዎች:
💰 ጠቅላላ ብድር: ባንኩ በግማሽ ዓመቱ በአጠቃላይ 321 ቢሊዮን ብር ብድር አቅርቧል።
🏭 የግሉ ዘርፍ ድርሻ: ከጠቅላላው ብድር ውስጥ 293.9 ቢሊዮን ብሩ (91%) ለግሉ ዘርፍ የተሰጠ ነው።
☪️ ሲቢኢ ኑር: ከወለድ ነጻ የባንክ አገልግሎት (CBE Noor) ተጠቃሚዎች 51.3 ቢሊዮን ብር የብድር አቅርቦት አግኝተዋል።
ብድሩ ለማን ቀረበ?
ለአምራች ኢንዱስትሪዎች
ለአስመጪ እና ላኪዎች
በአገልግሎት ዘርፍ ለተሰማሩ
ለሌሎች የኢንቨስትመንት መስኮች
ይህ እርምጃ የግሉን ዘርፍ የኢኮኖሚ ተሳትፎ ለማሳደግ ትልቅ ሚና ይጫወታል ተብሎ ይታመናል።
#cbe #commercialbankofethiopia #privatesector #loan #economy #ethiopia #cbenoor #investment
#ethiopia | "በግማሽ ዓመት 293.9 ቢሊዮን ብር ለግል ባለሀብቶች እና ድርጅቶች ቀርቧል"
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በተጠናቀቀው ግማሽ የበጀት ዓመት ያቀረበው የብድር መጠን ለግሉ ዘርፍ (Private Sector) ትልቅ ትኩረት የሰጠ መሆኑን ገለጸ።
ቁልፍ የብድር መረጃዎች:
💰 ጠቅላላ ብድር: ባንኩ በግማሽ ዓመቱ በአጠቃላይ 321 ቢሊዮን ብር ብድር አቅርቧል።
🏭 የግሉ ዘርፍ ድርሻ: ከጠቅላላው ብድር ውስጥ 293.9 ቢሊዮን ብሩ (91%) ለግሉ ዘርፍ የተሰጠ ነው።
☪️ ሲቢኢ ኑር: ከወለድ ነጻ የባንክ አገልግሎት (CBE Noor) ተጠቃሚዎች 51.3 ቢሊዮን ብር የብድር አቅርቦት አግኝተዋል።
ብድሩ ለማን ቀረበ?
ለአምራች ኢንዱስትሪዎች
ለአስመጪ እና ላኪዎች
በአገልግሎት ዘርፍ ለተሰማሩ
ለሌሎች የኢንቨስትመንት መስኮች
ይህ እርምጃ የግሉን ዘርፍ የኢኮኖሚ ተሳትፎ ለማሳደግ ትልቅ ሚና ይጫወታል ተብሎ ይታመናል።
#cbe #commercialbankofethiopia #privatesector #loan #economy #ethiopia #cbenoor #investment
8 months ago
ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የተሰጠ ጋዜጣዊ መግለጫ
መግለጫው እንደሚከተለው ቀርቧል
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የገንዘብ ፖሊሲ ኮሚቴ አራተኛ ስብሰባውን መስከረም 15 ቀን 2018 ዓ.ም አካሂዷል።
በተሻሻለው የባንኩ ማቋቋሚያ አዋጅ ቁጥር 1359/2025፣ አንቀጽ 23፣ በተሰጠው ተግባርና ኃላፊነት መሠረት የተቋቋመው የገንዘብ ፖሊሲ ኮሚቴ ከባንኩ ዋጋን ከማረጋጋት ቀዳሚ ዓላማ ጋር የተጣጣሙ የገንዘብ ፖሊሲ ምክረ ሐሳቦችን ለባንኩ የዳይሬክተሮች ቦርድ እያቀረበ ያስጸድቃል።
በዚህ ረገድ፣ ኮሚቴው የኢትዮጵያን የዋጋ ግሽበት፣ የፊስካል፣ የውጭ ኢኮኖሚ፣ የገንዘብ አቅርቦትና የፋይናንስ ዘርፍ አዝማሚያዎችን፣ አጠቃላይ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ አመልካቾችን እንዲሁም በሀገር ውስጥ የማክሮ ኢኮኖሚ ላይ ጉልህ አንደምታ ያላቸው ዓለም አቀፍ ሁኔታዎችን ይገመግማል። ከእነዚህ የማክሮ ኢኮኖሚያዊ ግምገማዎችና የቅርብ ጊዜ የወደፊት ትንበያዎች በመነሣትም በቀጣይ ተግባራዊ የሚደረጉ የፖሊሲ ምክረ-ሐሳቦችን ያቀርባል።
በዚሁ መሠረት፤ ኮሚቴው በውይይቱ ያካተታቸው ዐበይት ጉዳዮች የሚከተሉት ናቸው፡-
የዋጋ ግሽበት፡- ዓመታዊ የዋጋ ግሽበት በተከታታይ እየቀነሰ በመምጣት ነሐሴ ወር 2017 ዓ.ም መጨረሻ 13.6 በመቶ ደርሷል። በኮሚቴው ግምገማ መሠረት ለዋጋ ግሽበት መቀነስ ዐበይት ምክንያቶች ብሔራዊ ባንክ ተግባራዊ እያደረገ ያለው ጥብቅ የገንዘብ ፖሊሲ፣ የግብርና ምርታማነት መሻሻል እና መንግሥት ዋጋን ለማረጋጋት እየወሰዳቸው ያሉ አስተዳደራዊ እርምጃዎች ናቸው፡ የዋጋ ግሽበትን ከፋፍለን ስናይ፤ ምግብ-ነክ የዋጋ ግሽበት ነሐሴ ወር 2017 ዓ.ም መጨረሻ 127 በመቶ የደረሰ ሲሆን፣ ይህም ባለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወር ከነበረው የ18.8 በመቶ ጋር ሲነጻጸር ከፍተኛ ቅናሽ አሳይቷል። በአንጻሩ፣ ምግብ-ነክ ያልሆነ የዋጋ ግሽበት ካለፈው ዓመት ጋር ሲነጻጸር መጠነኛ ጭማሪ በማሳየት 15.1 በመቶ ሆኗል።
ለዚህም በቅርቡ የተካሄደው የውጭ ምንዛሪ ተመን ለውጥ ጫና በተወሰነ መልኩ አስተዋጽኦ አድርጓል። በተመሳሳይ መልኩ፣ ነሐሴ ወር 2017 ዓ.ም መጨረሻ ወርሃዊ የዋጋ ግሽበት ወደ 11 በመቶ ዝቅ ማለቱ የዋጋ ግሽበቱ በኢኮኖሚ ላይ የሚያሳድረው ተጽእኖ እየቀለለ መሄዱን ያመላክታል።
የኢኮኖሚ እንቅስቃሴና ዕድገት፡- ኮሚቴው የሀገር ውስጥ የኢኮኖሚ ዕድገት ተጠናክሮ መቀጠሉን ተገንዝቧል። የብሔራዊ ባንክ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ አመላካቾች (Composite |ndex of Economic Activities) የተጠናከረ የኢኮኖሚ ዕድገት መኖሩን ያሳያሉ።
ለዚህም በግብርናው ዘርፍ የሚታየው ምርትና ምርታማነት መጨመር፣ ከውጭ ምንዛሪ ለውጡ ጋር ተያይዞ የኢንዱስትሪው ዘርፍ ምርት ማደግ፤ እንዲሁም የወጪ ሸቀጦች ንግድ በተለይም ወደ ውጭ የሚላከው ቡና እና ወርቅ ከፍተኛ እመርታ ማሳየት ለኢኮኖሚ ዕድገቱ አዎንታዊ አስተዋጽኦ አድርገዋል ። በአንጻሩ፣ ወደ ሃገር ውስጥ በሚገቡ ሸቀጦች ማለትም በከፊል ያለቀላቸው እቃዎች እና የፍጆታ ሸቀጦች ላይ መቀዛቀዝ ታይቷል።
የገንዘብ ሁኔታ፡- በገንዘብ ዝውውር አመልካቾች ረገድ ፈጣን ዕድገት ተስተውሏል። ለዚህም የብድር ዕድገት ገደቡ ላላ መደረጉ እንዲሁም የፊስካል እና የውጭ ዘርፍ ዕድገት ማሳየታቸው አስተዋጽኦ አድርገዋል።
በመሆኑም፣ ነሐሴ ወር 2017 ዓ.ም መጨረሻ በኢኮኖሚ ውስጥ የሚዘዋወረው የጠቅላላ ገንዘብ አቅርቦት (broad money supply) 23.1 በመቶ፣ መሠረታዊ ገንዘብ (base money) 70.7 በመቶ፤ የሀገር ውስጥ ብድር 14 በመቶ ዓመታዊ ዕድገት አሳይተዋል። ከዚህ ሌላ፣ አጠቃላይ የባንኮች የብድር ክምችት ከሰኔ ወር 2017 ጋር ሲነጻጸር 5.4 በመቶ ጨምሯል ።
ለመሠረታዊ ገንዘብ ከፍተኛ ዕድገት ዋናው ምክንያት ከወርቅ ግዢ ጋር በተያያዘ የብሔራዊ ባንክ የውጪ ምንዛሪ ክምችት በመጨመሩ እና ከዚህም የተነሣ ወደ ባንኮች የገባው የብር ፍሰት መጠን ከፍ በማለቱ ነው። ይሁን እንጂ፣ የብድር ዕድገት ገደብ ፖሊሲ መኖሩ የጠቅላላ ገንዘብ ዕድገቱ የተለጠጠ እንዳይሆን አድርጎታል።
የወለድ ተመን ሁኔታ፡- የዕድገት አዝማሚያ ከፖሊሲ የወለድ ተመን ጋር የተቀራረበ መሆኑን፣ እንዲሁም የዋጋ ግሽበትን ታሳቢ ካደረገው የወለድ ተመን ጋር ሲነጻጸር ከዜሮ በላይ ሆኖ መቀጠሉን ኮሚቴዉ ተገንዝቧል። ይህም አዝማሚያ ለገንዘብ ገበያ መነቃቃት አስተዋጽኦ እንዳለው መረዳት ተችሏል።
ለምሳሌ፣ የ91-ቀን የመንግሥት ግምጃ ቤት ሰነድ አማካይ የወለድ ተመን ሰኔ ወር 2017 ከነበረበት 17.6 በመቶ በነሐሴ ወር 2017 መጨረሻ ወደ 15.0 ዝቅ ብሏል። በተመሳሳይ በኢኮኖሚው ውስጥ ያለውን የገንዘብ ዋጋ የሚያመላክተው የ7-ቀን የባንክ ለባንክ ግብይት አማካኝ የወለድ ተመን በሚፈለገው የወለድ ተመን ክልል (nterest Rate Corridor) ውስጥ እንዲቆይ ብሔራዊ ባንክ ከባንኮች ጋር የገንዘብ ግብይት (Open Market Operations) እያደረገ ይገኛል።
በመሆኑም፣ በነሐሴ ወር 2017 መጨረሻ የ7-ቀን የባንክ ለባንክ ግብይት አማካኝ የወለድ ተመን ወደ 13.7 በመቶ ዝቅ ያለ ሲሆን፣ ይህም ብሔራዊ ባንክ ባስቀመጠው የወለድ ተመን ክልል ውስጥ መሆኑ ታውቋል። ጥቅምት 2017 ዓ.ም የተጀመረው በባንኮች መካከል የሚደረግ የገንዘብ ግብይት ከፍተኛ ዕድገት በማሳየት በነሐሴ ወር 2017 መጨረሻ ብር 945.1 ቢሊዮን ደርሷል።
የፋይናንስ ዘርፍ መረጋጋት፡- የባንክ ዘርፍ ዝቅተኛ የተበላሸ ብድር እና በቂ ካፒታል ያስመዘገበ በመሆኑ ጤናማና የተረጋጋ መሆኑን፣ ነገር ግን፣ በአንዳንድ ባንኮች ዘንድ በተወሰነ መልኩ የጥሬ ገንዘብ አከል (liquidity) እጥረት መኖሩን ኮሚቴው አስተውሏል። ይህም የሆነዉ በባንኮች ዘንድ በሚታየው ከፍተኛ የብድርና የተቀማጭ ሂሳብ (loan to deposit ratio) ጥምርታ ምክንያት ቢሆንም አሁን ላይ ችግሩ በባንክ ለባንክ የገንዘብ ገበያ (nterbank Money Market) እና በብሔራዊ ባንክ ዕለታዊ የብድር አገልግሎት መፍትሔ እያገኘ ነው።
የፊስካል ሁኔታ፡- የፊስካል ፖሊሲ ጥንቃቄ የተሞላበትና ከብሔራዊ ባንክ ጥብቅ የገንዘብ ፖሊሲ ጋር የተጣጣመ መሆኑን ኮሚቴው ተገንዝቧል። ልክ እንደባለፈዉ በጀት ዓመት ሁሉ በተያዘው የበጀት ዓመት የመጀመሪያ ሁለት ወራትም መንግሥት ለበጀት ጉድለት ማሟያ ከብሔራዊ ባንክ ምንም ብድር አለመውሰዱ የብሔራዊ ባንክን የገንዘብ ፖሊሲ አቋም በእጅጉ የሚደግፍ ክስተት ሆኖ ቀጥሏል።
የውጭ ኢኮኖሚ ዘርፍ፡- በሐምሌ ወር 2016 ከተወሰደው ሁሉን አቀፍ የኢኮኖሚ ማሻሻያ ጋር ተያይዞ የውጭ ኢኮኖሚ ዘርፉ በበርካታ መመዘኛዎች ትልቅ እምርታ እያሳየ መሄዱን ኮሚቴው ተገንዝቧል። ለምሳሌ፣ በወጪ ንግድ በተለይም በወርቅና በቡና ንግድ፣ በግለሰብ ሐዋላ እንዲሁም በተጣራ የአገልግሎት ንግድ ከፍተኛ ዕድገት ታይቷል። በመሆኑም፣ የከረንት አካውንት ጉድለት ተሸሽሏል እንዲሁም አጠቃላይ የክፍያ ሚዛን ትርፍ አሳይተዋል።
ዓለም አቀፍ ሁኔታዎች፡- የዓለም አቀፍ የኢኮኖሚ ዕድገት ካለፈው ትንበያ በተወሰነ መልኩ ከፍ እንደሚል፣ እ.ኤ.አ በ2025 ዕድገቱ 3.0 በመቶ፤ በ2026 ደግሞ 3.1 በመቶ እንደሚሆን የዓለም የገንዘብ ድርጅት (IMF) መረጃ ያመላክታል። ይህም የሆነው ከፍተኛ የታሪፍ ጭማሪ እንደሚኖር፣ በከፊል ከአሜሪካን ዶላር ዋጋ መዳከም ጋር ተያይዞ የተሻሻለ የፋይናንስ ሁኔታ እንደሚፈጠር እንዲሁም በብዙ ትላልቅ ኢኮኖሚዎች ዘንድ የፊስካል ዕድገት እንደሚኖር ታሳቢ በመደረጉ ነው።
ከዚህ ሌላ፣ የዓለም አቀፍ የዋጋ ግሽበት እ.ኤ.አ በ2025 ወደ 4.2 በመቶ ፣ እ.ኤ.አ በ2026 ደግሞ ወደ 3.6 በመቶ ዝቅ እንደሚል ይገመታል። ይህም የፍላጎት መቀዛቀዝንና የነዳጅ ዋጋ ማሽቆልቆልን የሚያመለክት ነው። ሆኖም፣ የታሪፍ መጨመርና የአቅርቦት እጥረት በአሜሪካን ኢኮኖሚ ላይ ተጽእኖ እንደሚያሳድርና እ.ኤ.አ. በ2025 ሁለተኛ አጋማሽ ለዋጋ ግሽበት አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ይገመታል።
የገንዘብ ፖሊሲ ኮሚቴ ግምገማና የውሳኔ ሐሳብ
በሀገራችን የዋጋ ግሽበት በተከታታይ እየቀነሰ መምጣቱ አበረታች ቢሆንም፣ አሁንም ቢሆን ከሚጠበቀው የነጠላ አሃዝ አኳያ ከፍ ያለ መሆኑን ኮሚቴው ተገንዝቧል። በመሆኑም፣ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ እየወሰደ ያለው ጥብቅ የገንዘብ ፖሊሲን ማስቀጠሉ የዋጋ ግሽበቱን ለማርገብ ከፍተኛ ሚና እንደሚኖረው ኮሚቴው በጽኑ ያምናል።
በባንኮች ዓመታዊ የብድር ዕድገት ላይ የተጣለዉ ገደብ መነሣት ባንኩ ከሚከተለዉ የገንዘብ ፖሊሲ ማዕቀፍ አንጻር አግባብ መሆኑን ኮሚቴው ቢገነዘብም፣ አካሄዱ ከፍተኛ ትኩረት እና ጥንቃቄ የተሞላበት መሆን እንዳለበት መግባባት ላይ ተደርሷል። ይህም የሆነዉ በዋናነት ልቅ የገንዘብ ፖሊሲ የሚያስከትለውን ጉዳት ለመከላከልና የተረጋጋ የፋይናንስ ሥርዓት እንዲኖር ለማድረግ ነው።
ከዚህም ግምገማ በመነሣት ኮሚቴው ከዚህ የሚከተሉትን የገንዘብ ፖሊሲ ምክረ ሐሳቦች ለቦርድ አቅርቦ አስወስኗል፡-
አንደኛ፤ የብሔራዊ ባንክ የፖሊሲ ተመን (National Bank Bate) አሁን ባለበት 15 በመቶ እንዲቆይ፣ ብሔራዊ ባንክ ለሚሰጣቸው የተቀማጭ ሂሳብ አገልግሎት (standing deposit facility)፣እና የብድር አገልግሎት (standing lending facility) የሚከፈሉ የወለድ ተመኖች ባሉበት እንዲቀጥሉ፣ እንዲሁም ባንኮች በብሔራዊ ባንክ የሚያስቀምጡት የግዴታ መጠባበቂያ ምጣኔ በነበረበት እንዲቆይ ተወስኗል።
ሁለተኛ፤ የባንኮች የብድር ዕድገት ገደብ መነሣት የብሔራዊ ባንክን የገንዘብ ፖሊሲ አቋም ለማመልከትና የገንዘብ ፖሊሲ መዋቅሩን የተሻለ ለማድረግ እንደሚረዳ ቢታመንም፣ አሁን ላይ እየተስተዋለ ያለውን የዋጋ ግሽበት የመርገብ አዝማሚያ ለማስቀጠልና የፋይናንስ ዘርፉን ጤናማነት ለመጠበቅ በመስከረም ወር ላይ ሊነሣ ይችላል ተብሎ የተገመተዉ የባንኮች ዓመታዊ የብድር ዕድገት ጣሪያን ሙሉ ለሙሉ ከማንሣት ይልቅ ገደቡ ለጊዜው ከ18 በመቶ ወደ 24 በመቶ ከፍ እንዲል ተወስኗል። የገንዘብ ፖሊሲ ኮሚቴው ይህንን ጉዳይ በቀጣይ ስብሰባዎቹ ገምግሞ የውሳኔ ሐሳብ የሚያቀርብ ይሆናል።
ሶስተኛ፤ ብሔራዊ ባንክ የዋጋ ግሽበቱ በሚፈለገው ልክ እንዲሆን ለማስቻል እንደ አስፈላጊነቱ ገበያ-መር የሆኑ የገንዘብ ፖሊሲ መሣሪያዎችን በተናጠልም ሆነ በቅንጅት በቀጣይነት የሚጠቀም ይሆናል። እነዚህ የገንዘብ ፖሊሲ መሣሪያዎች የብሔራዊ ባንክ የወለድ ተመን፣ ከባንኮች ጋር የሚደረግ የገንዘብ ግብይት (Open Market Operations)፣ የውጭ ምንዛሪ ገበያ (foreign exchange interventions) እንዲሁም ባንኮች በብሔራዊ ባንክ የሚያስቀምጡት የግዴታ መጠባበቂያ ምጣኔ ይሆናሉ።
በመጨረሻም ቀጣዩ የኮሚቴው ስብሰባ ታህሳስ ወር 2018 እንዲሆን ተወስኗል።
የገንዘብ ፖሊሲ ኮሚቴ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ
መስከረም 19 ቀን 2018
መግለጫው እንደሚከተለው ቀርቧል
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የገንዘብ ፖሊሲ ኮሚቴ አራተኛ ስብሰባውን መስከረም 15 ቀን 2018 ዓ.ም አካሂዷል።
በተሻሻለው የባንኩ ማቋቋሚያ አዋጅ ቁጥር 1359/2025፣ አንቀጽ 23፣ በተሰጠው ተግባርና ኃላፊነት መሠረት የተቋቋመው የገንዘብ ፖሊሲ ኮሚቴ ከባንኩ ዋጋን ከማረጋጋት ቀዳሚ ዓላማ ጋር የተጣጣሙ የገንዘብ ፖሊሲ ምክረ ሐሳቦችን ለባንኩ የዳይሬክተሮች ቦርድ እያቀረበ ያስጸድቃል።
በዚህ ረገድ፣ ኮሚቴው የኢትዮጵያን የዋጋ ግሽበት፣ የፊስካል፣ የውጭ ኢኮኖሚ፣ የገንዘብ አቅርቦትና የፋይናንስ ዘርፍ አዝማሚያዎችን፣ አጠቃላይ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ አመልካቾችን እንዲሁም በሀገር ውስጥ የማክሮ ኢኮኖሚ ላይ ጉልህ አንደምታ ያላቸው ዓለም አቀፍ ሁኔታዎችን ይገመግማል። ከእነዚህ የማክሮ ኢኮኖሚያዊ ግምገማዎችና የቅርብ ጊዜ የወደፊት ትንበያዎች በመነሣትም በቀጣይ ተግባራዊ የሚደረጉ የፖሊሲ ምክረ-ሐሳቦችን ያቀርባል።
በዚሁ መሠረት፤ ኮሚቴው በውይይቱ ያካተታቸው ዐበይት ጉዳዮች የሚከተሉት ናቸው፡-
የዋጋ ግሽበት፡- ዓመታዊ የዋጋ ግሽበት በተከታታይ እየቀነሰ በመምጣት ነሐሴ ወር 2017 ዓ.ም መጨረሻ 13.6 በመቶ ደርሷል። በኮሚቴው ግምገማ መሠረት ለዋጋ ግሽበት መቀነስ ዐበይት ምክንያቶች ብሔራዊ ባንክ ተግባራዊ እያደረገ ያለው ጥብቅ የገንዘብ ፖሊሲ፣ የግብርና ምርታማነት መሻሻል እና መንግሥት ዋጋን ለማረጋጋት እየወሰዳቸው ያሉ አስተዳደራዊ እርምጃዎች ናቸው፡ የዋጋ ግሽበትን ከፋፍለን ስናይ፤ ምግብ-ነክ የዋጋ ግሽበት ነሐሴ ወር 2017 ዓ.ም መጨረሻ 127 በመቶ የደረሰ ሲሆን፣ ይህም ባለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወር ከነበረው የ18.8 በመቶ ጋር ሲነጻጸር ከፍተኛ ቅናሽ አሳይቷል። በአንጻሩ፣ ምግብ-ነክ ያልሆነ የዋጋ ግሽበት ካለፈው ዓመት ጋር ሲነጻጸር መጠነኛ ጭማሪ በማሳየት 15.1 በመቶ ሆኗል።
ለዚህም በቅርቡ የተካሄደው የውጭ ምንዛሪ ተመን ለውጥ ጫና በተወሰነ መልኩ አስተዋጽኦ አድርጓል። በተመሳሳይ መልኩ፣ ነሐሴ ወር 2017 ዓ.ም መጨረሻ ወርሃዊ የዋጋ ግሽበት ወደ 11 በመቶ ዝቅ ማለቱ የዋጋ ግሽበቱ በኢኮኖሚ ላይ የሚያሳድረው ተጽእኖ እየቀለለ መሄዱን ያመላክታል።
የኢኮኖሚ እንቅስቃሴና ዕድገት፡- ኮሚቴው የሀገር ውስጥ የኢኮኖሚ ዕድገት ተጠናክሮ መቀጠሉን ተገንዝቧል። የብሔራዊ ባንክ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ አመላካቾች (Composite |ndex of Economic Activities) የተጠናከረ የኢኮኖሚ ዕድገት መኖሩን ያሳያሉ።
ለዚህም በግብርናው ዘርፍ የሚታየው ምርትና ምርታማነት መጨመር፣ ከውጭ ምንዛሪ ለውጡ ጋር ተያይዞ የኢንዱስትሪው ዘርፍ ምርት ማደግ፤ እንዲሁም የወጪ ሸቀጦች ንግድ በተለይም ወደ ውጭ የሚላከው ቡና እና ወርቅ ከፍተኛ እመርታ ማሳየት ለኢኮኖሚ ዕድገቱ አዎንታዊ አስተዋጽኦ አድርገዋል ። በአንጻሩ፣ ወደ ሃገር ውስጥ በሚገቡ ሸቀጦች ማለትም በከፊል ያለቀላቸው እቃዎች እና የፍጆታ ሸቀጦች ላይ መቀዛቀዝ ታይቷል።
የገንዘብ ሁኔታ፡- በገንዘብ ዝውውር አመልካቾች ረገድ ፈጣን ዕድገት ተስተውሏል። ለዚህም የብድር ዕድገት ገደቡ ላላ መደረጉ እንዲሁም የፊስካል እና የውጭ ዘርፍ ዕድገት ማሳየታቸው አስተዋጽኦ አድርገዋል።
በመሆኑም፣ ነሐሴ ወር 2017 ዓ.ም መጨረሻ በኢኮኖሚ ውስጥ የሚዘዋወረው የጠቅላላ ገንዘብ አቅርቦት (broad money supply) 23.1 በመቶ፣ መሠረታዊ ገንዘብ (base money) 70.7 በመቶ፤ የሀገር ውስጥ ብድር 14 በመቶ ዓመታዊ ዕድገት አሳይተዋል። ከዚህ ሌላ፣ አጠቃላይ የባንኮች የብድር ክምችት ከሰኔ ወር 2017 ጋር ሲነጻጸር 5.4 በመቶ ጨምሯል ።
ለመሠረታዊ ገንዘብ ከፍተኛ ዕድገት ዋናው ምክንያት ከወርቅ ግዢ ጋር በተያያዘ የብሔራዊ ባንክ የውጪ ምንዛሪ ክምችት በመጨመሩ እና ከዚህም የተነሣ ወደ ባንኮች የገባው የብር ፍሰት መጠን ከፍ በማለቱ ነው። ይሁን እንጂ፣ የብድር ዕድገት ገደብ ፖሊሲ መኖሩ የጠቅላላ ገንዘብ ዕድገቱ የተለጠጠ እንዳይሆን አድርጎታል።
የወለድ ተመን ሁኔታ፡- የዕድገት አዝማሚያ ከፖሊሲ የወለድ ተመን ጋር የተቀራረበ መሆኑን፣ እንዲሁም የዋጋ ግሽበትን ታሳቢ ካደረገው የወለድ ተመን ጋር ሲነጻጸር ከዜሮ በላይ ሆኖ መቀጠሉን ኮሚቴዉ ተገንዝቧል። ይህም አዝማሚያ ለገንዘብ ገበያ መነቃቃት አስተዋጽኦ እንዳለው መረዳት ተችሏል።
ለምሳሌ፣ የ91-ቀን የመንግሥት ግምጃ ቤት ሰነድ አማካይ የወለድ ተመን ሰኔ ወር 2017 ከነበረበት 17.6 በመቶ በነሐሴ ወር 2017 መጨረሻ ወደ 15.0 ዝቅ ብሏል። በተመሳሳይ በኢኮኖሚው ውስጥ ያለውን የገንዘብ ዋጋ የሚያመላክተው የ7-ቀን የባንክ ለባንክ ግብይት አማካኝ የወለድ ተመን በሚፈለገው የወለድ ተመን ክልል (nterest Rate Corridor) ውስጥ እንዲቆይ ብሔራዊ ባንክ ከባንኮች ጋር የገንዘብ ግብይት (Open Market Operations) እያደረገ ይገኛል።
በመሆኑም፣ በነሐሴ ወር 2017 መጨረሻ የ7-ቀን የባንክ ለባንክ ግብይት አማካኝ የወለድ ተመን ወደ 13.7 በመቶ ዝቅ ያለ ሲሆን፣ ይህም ብሔራዊ ባንክ ባስቀመጠው የወለድ ተመን ክልል ውስጥ መሆኑ ታውቋል። ጥቅምት 2017 ዓ.ም የተጀመረው በባንኮች መካከል የሚደረግ የገንዘብ ግብይት ከፍተኛ ዕድገት በማሳየት በነሐሴ ወር 2017 መጨረሻ ብር 945.1 ቢሊዮን ደርሷል።
የፋይናንስ ዘርፍ መረጋጋት፡- የባንክ ዘርፍ ዝቅተኛ የተበላሸ ብድር እና በቂ ካፒታል ያስመዘገበ በመሆኑ ጤናማና የተረጋጋ መሆኑን፣ ነገር ግን፣ በአንዳንድ ባንኮች ዘንድ በተወሰነ መልኩ የጥሬ ገንዘብ አከል (liquidity) እጥረት መኖሩን ኮሚቴው አስተውሏል። ይህም የሆነዉ በባንኮች ዘንድ በሚታየው ከፍተኛ የብድርና የተቀማጭ ሂሳብ (loan to deposit ratio) ጥምርታ ምክንያት ቢሆንም አሁን ላይ ችግሩ በባንክ ለባንክ የገንዘብ ገበያ (nterbank Money Market) እና በብሔራዊ ባንክ ዕለታዊ የብድር አገልግሎት መፍትሔ እያገኘ ነው።
የፊስካል ሁኔታ፡- የፊስካል ፖሊሲ ጥንቃቄ የተሞላበትና ከብሔራዊ ባንክ ጥብቅ የገንዘብ ፖሊሲ ጋር የተጣጣመ መሆኑን ኮሚቴው ተገንዝቧል። ልክ እንደባለፈዉ በጀት ዓመት ሁሉ በተያዘው የበጀት ዓመት የመጀመሪያ ሁለት ወራትም መንግሥት ለበጀት ጉድለት ማሟያ ከብሔራዊ ባንክ ምንም ብድር አለመውሰዱ የብሔራዊ ባንክን የገንዘብ ፖሊሲ አቋም በእጅጉ የሚደግፍ ክስተት ሆኖ ቀጥሏል።
የውጭ ኢኮኖሚ ዘርፍ፡- በሐምሌ ወር 2016 ከተወሰደው ሁሉን አቀፍ የኢኮኖሚ ማሻሻያ ጋር ተያይዞ የውጭ ኢኮኖሚ ዘርፉ በበርካታ መመዘኛዎች ትልቅ እምርታ እያሳየ መሄዱን ኮሚቴው ተገንዝቧል። ለምሳሌ፣ በወጪ ንግድ በተለይም በወርቅና በቡና ንግድ፣ በግለሰብ ሐዋላ እንዲሁም በተጣራ የአገልግሎት ንግድ ከፍተኛ ዕድገት ታይቷል። በመሆኑም፣ የከረንት አካውንት ጉድለት ተሸሽሏል እንዲሁም አጠቃላይ የክፍያ ሚዛን ትርፍ አሳይተዋል።
ዓለም አቀፍ ሁኔታዎች፡- የዓለም አቀፍ የኢኮኖሚ ዕድገት ካለፈው ትንበያ በተወሰነ መልኩ ከፍ እንደሚል፣ እ.ኤ.አ በ2025 ዕድገቱ 3.0 በመቶ፤ በ2026 ደግሞ 3.1 በመቶ እንደሚሆን የዓለም የገንዘብ ድርጅት (IMF) መረጃ ያመላክታል። ይህም የሆነው ከፍተኛ የታሪፍ ጭማሪ እንደሚኖር፣ በከፊል ከአሜሪካን ዶላር ዋጋ መዳከም ጋር ተያይዞ የተሻሻለ የፋይናንስ ሁኔታ እንደሚፈጠር እንዲሁም በብዙ ትላልቅ ኢኮኖሚዎች ዘንድ የፊስካል ዕድገት እንደሚኖር ታሳቢ በመደረጉ ነው።
ከዚህ ሌላ፣ የዓለም አቀፍ የዋጋ ግሽበት እ.ኤ.አ በ2025 ወደ 4.2 በመቶ ፣ እ.ኤ.አ በ2026 ደግሞ ወደ 3.6 በመቶ ዝቅ እንደሚል ይገመታል። ይህም የፍላጎት መቀዛቀዝንና የነዳጅ ዋጋ ማሽቆልቆልን የሚያመለክት ነው። ሆኖም፣ የታሪፍ መጨመርና የአቅርቦት እጥረት በአሜሪካን ኢኮኖሚ ላይ ተጽእኖ እንደሚያሳድርና እ.ኤ.አ. በ2025 ሁለተኛ አጋማሽ ለዋጋ ግሽበት አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ይገመታል።
የገንዘብ ፖሊሲ ኮሚቴ ግምገማና የውሳኔ ሐሳብ
በሀገራችን የዋጋ ግሽበት በተከታታይ እየቀነሰ መምጣቱ አበረታች ቢሆንም፣ አሁንም ቢሆን ከሚጠበቀው የነጠላ አሃዝ አኳያ ከፍ ያለ መሆኑን ኮሚቴው ተገንዝቧል። በመሆኑም፣ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ እየወሰደ ያለው ጥብቅ የገንዘብ ፖሊሲን ማስቀጠሉ የዋጋ ግሽበቱን ለማርገብ ከፍተኛ ሚና እንደሚኖረው ኮሚቴው በጽኑ ያምናል።
በባንኮች ዓመታዊ የብድር ዕድገት ላይ የተጣለዉ ገደብ መነሣት ባንኩ ከሚከተለዉ የገንዘብ ፖሊሲ ማዕቀፍ አንጻር አግባብ መሆኑን ኮሚቴው ቢገነዘብም፣ አካሄዱ ከፍተኛ ትኩረት እና ጥንቃቄ የተሞላበት መሆን እንዳለበት መግባባት ላይ ተደርሷል። ይህም የሆነዉ በዋናነት ልቅ የገንዘብ ፖሊሲ የሚያስከትለውን ጉዳት ለመከላከልና የተረጋጋ የፋይናንስ ሥርዓት እንዲኖር ለማድረግ ነው።
ከዚህም ግምገማ በመነሣት ኮሚቴው ከዚህ የሚከተሉትን የገንዘብ ፖሊሲ ምክረ ሐሳቦች ለቦርድ አቅርቦ አስወስኗል፡-
አንደኛ፤ የብሔራዊ ባንክ የፖሊሲ ተመን (National Bank Bate) አሁን ባለበት 15 በመቶ እንዲቆይ፣ ብሔራዊ ባንክ ለሚሰጣቸው የተቀማጭ ሂሳብ አገልግሎት (standing deposit facility)፣እና የብድር አገልግሎት (standing lending facility) የሚከፈሉ የወለድ ተመኖች ባሉበት እንዲቀጥሉ፣ እንዲሁም ባንኮች በብሔራዊ ባንክ የሚያስቀምጡት የግዴታ መጠባበቂያ ምጣኔ በነበረበት እንዲቆይ ተወስኗል።
ሁለተኛ፤ የባንኮች የብድር ዕድገት ገደብ መነሣት የብሔራዊ ባንክን የገንዘብ ፖሊሲ አቋም ለማመልከትና የገንዘብ ፖሊሲ መዋቅሩን የተሻለ ለማድረግ እንደሚረዳ ቢታመንም፣ አሁን ላይ እየተስተዋለ ያለውን የዋጋ ግሽበት የመርገብ አዝማሚያ ለማስቀጠልና የፋይናንስ ዘርፉን ጤናማነት ለመጠበቅ በመስከረም ወር ላይ ሊነሣ ይችላል ተብሎ የተገመተዉ የባንኮች ዓመታዊ የብድር ዕድገት ጣሪያን ሙሉ ለሙሉ ከማንሣት ይልቅ ገደቡ ለጊዜው ከ18 በመቶ ወደ 24 በመቶ ከፍ እንዲል ተወስኗል። የገንዘብ ፖሊሲ ኮሚቴው ይህንን ጉዳይ በቀጣይ ስብሰባዎቹ ገምግሞ የውሳኔ ሐሳብ የሚያቀርብ ይሆናል።
ሶስተኛ፤ ብሔራዊ ባንክ የዋጋ ግሽበቱ በሚፈለገው ልክ እንዲሆን ለማስቻል እንደ አስፈላጊነቱ ገበያ-መር የሆኑ የገንዘብ ፖሊሲ መሣሪያዎችን በተናጠልም ሆነ በቅንጅት በቀጣይነት የሚጠቀም ይሆናል። እነዚህ የገንዘብ ፖሊሲ መሣሪያዎች የብሔራዊ ባንክ የወለድ ተመን፣ ከባንኮች ጋር የሚደረግ የገንዘብ ግብይት (Open Market Operations)፣ የውጭ ምንዛሪ ገበያ (foreign exchange interventions) እንዲሁም ባንኮች በብሔራዊ ባንክ የሚያስቀምጡት የግዴታ መጠባበቂያ ምጣኔ ይሆናሉ።
በመጨረሻም ቀጣዩ የኮሚቴው ስብሰባ ታህሳስ ወር 2018 እንዲሆን ተወስኗል።
የገንዘብ ፖሊሲ ኮሚቴ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ
መስከረም 19 ቀን 2018
Sponsored by
Surafel