4 months ago
ድጋፍ ማይክሮ ፋይናንስ በአጭር ጊዜ ውስጥ ስኬታማ መሆኑን ገለጸ
#ethiopia | የድጋፍ ማይክሮ ፋይናንስ ተቋም ባለፉት ጥቂት ወራት ባሳየው አስደናቂ እድገት፣ ከደንበኞች የሰበሰበው የተቀማጭ ገንዘብ መጠን ከ1 ቢሊዮን ብር በላይ መሻገሩን አስታወቀ።
ተቋሙ ዛሬ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ፣ ይህ ስኬት በደንበኞች ዘንድ ያለውን ጠንካራ አመኔታ እና የጀመረው የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ውጤታማነት ማሳያ መሆኑን ገልጿል።
ድጋፍ ማይክሮ ፋይናንስ፣ ላለፉት ዓመታት ሲከተለው የነበረውን የተለመደ አሠራር በመቀየር፣ ከሁለት ዓመት ወዲህ ትኩረቱን በዲጂታል ፋይናንሲንግ ላይ ማድረጉ ተገልጿል። በተለይም ባለፈው አንድ ዓመት ውስጥ በተከናወኑ ሥራዎች በአሁኑ ወቅት በወር ውስጥ እስከ 300 ሚሊዮን ብር ቁጠባ የመሰብሰብ አቅም ላይ መደረሱ ተጠቁሟል።
የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ደረጄ ቱሪ እንደገለጹት “ይህ ውጤት የገንዘብ ስኬት ብቻ ሳይሆን ደንበኞቻችን በእኛ ላይ ያላቸው እምነት ማረጋገጫ ነው ብለዋል።
የድጋፍ ቺፍ ኦፕሬሽን ኦፊሰር አቶ ምርቱ ከበደ በበኩላቸው፣ ተቋሙ በአዲስ አበባ፣ ባህርዳር፣ ሀዋሳ እና አዳማ የሚገኙ 8 ቅርንጫፎች ቢኖሩትም፣ አገልግሎቱ ግን በመላ ሀገሪቱ ተደራሽ መሆኑን ገልጸዋል።
በመላ ሀገሪቱ በሚገኙ የዞን እና የወረዳ ከተሞች የተሰማሩ ከ300 በላይ የሙሉ ጊዜ የብድር መኮንኖች እና ኤጀንቶች አሉት።
የአሠራር ዘይቤ፦ ደንበኞች ከሥራ ገበታቸው ሳይነቀሳቀሱ ባሉበት ሆነው በዲጂታል አማራጭ የብድር እና የቁጠባ አገልግሎት እንዲያገኙ ይደረጋል።
ተቋሙ የሰበሰበውን ተቀማጭ ገንዘብ መልሶ ለጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች፣ ለደመወዝ ከፋዮች እና የሥራ ዕድል ፈጠራ ላይ ለተሰማሩ የንግድ ዘርፎች በብድር መልክ በማቅረብ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴውን እያገዘ እንደሚገኝ ተመላክቷል።
#digafmfi #ethiopiafinance #microfinance #digitalbanking #financialinclusion #trustandgrowth
#ethiopia | የድጋፍ ማይክሮ ፋይናንስ ተቋም ባለፉት ጥቂት ወራት ባሳየው አስደናቂ እድገት፣ ከደንበኞች የሰበሰበው የተቀማጭ ገንዘብ መጠን ከ1 ቢሊዮን ብር በላይ መሻገሩን አስታወቀ።
ተቋሙ ዛሬ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ፣ ይህ ስኬት በደንበኞች ዘንድ ያለውን ጠንካራ አመኔታ እና የጀመረው የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ውጤታማነት ማሳያ መሆኑን ገልጿል።
ድጋፍ ማይክሮ ፋይናንስ፣ ላለፉት ዓመታት ሲከተለው የነበረውን የተለመደ አሠራር በመቀየር፣ ከሁለት ዓመት ወዲህ ትኩረቱን በዲጂታል ፋይናንሲንግ ላይ ማድረጉ ተገልጿል። በተለይም ባለፈው አንድ ዓመት ውስጥ በተከናወኑ ሥራዎች በአሁኑ ወቅት በወር ውስጥ እስከ 300 ሚሊዮን ብር ቁጠባ የመሰብሰብ አቅም ላይ መደረሱ ተጠቁሟል።
የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ደረጄ ቱሪ እንደገለጹት “ይህ ውጤት የገንዘብ ስኬት ብቻ ሳይሆን ደንበኞቻችን በእኛ ላይ ያላቸው እምነት ማረጋገጫ ነው ብለዋል።
የድጋፍ ቺፍ ኦፕሬሽን ኦፊሰር አቶ ምርቱ ከበደ በበኩላቸው፣ ተቋሙ በአዲስ አበባ፣ ባህርዳር፣ ሀዋሳ እና አዳማ የሚገኙ 8 ቅርንጫፎች ቢኖሩትም፣ አገልግሎቱ ግን በመላ ሀገሪቱ ተደራሽ መሆኑን ገልጸዋል።
በመላ ሀገሪቱ በሚገኙ የዞን እና የወረዳ ከተሞች የተሰማሩ ከ300 በላይ የሙሉ ጊዜ የብድር መኮንኖች እና ኤጀንቶች አሉት።
የአሠራር ዘይቤ፦ ደንበኞች ከሥራ ገበታቸው ሳይነቀሳቀሱ ባሉበት ሆነው በዲጂታል አማራጭ የብድር እና የቁጠባ አገልግሎት እንዲያገኙ ይደረጋል።
ተቋሙ የሰበሰበውን ተቀማጭ ገንዘብ መልሶ ለጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች፣ ለደመወዝ ከፋዮች እና የሥራ ዕድል ፈጠራ ላይ ለተሰማሩ የንግድ ዘርፎች በብድር መልክ በማቅረብ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴውን እያገዘ እንደሚገኝ ተመላክቷል።
#digafmfi #ethiopiafinance #microfinance #digitalbanking #financialinclusion #trustandgrowth
4 months ago
ድሬ ማይክሮ ፋይናንስ በአዲስ አበባ የመጀመሪያውን ቅርንጫፉን በይፋ አስመረቀ
#ethiopia | በምስራቅ ኢትዮጵያ በፋይናንስ ተደራሽነት ላይ ከፍተኛ አሻራ በማሳረፍ የሚታወቀው ድሬ ማይክሮ ፋይናንስ፣ አገልግሎቱን ወደ መዲናዋ አዲስ አበባ በማስፋት የመጀመሪያ የሆነውን የቦሌ ሚካኤል ቅርንጫፍ በዛሬው ዕለት በደማቅ ስነ-ስርዓት አስመረቀ።
ተቋሙ አዲስ አበባን ጨምሮ በድሬዳዋ፣ በሐረር፣ በጅግጅጋ እና በሀሮማያ ከተሞች ተደራሽነቱን በማስፋት፣ ለህብረተሰቡ የፋይናንስ አገልግሎትን በእኩልነት ለማዳረስ እየሰራ መሆኑ በምረቃው ላይ ተገልጿል።
በተለይም በትልልቅ የፋይናንስ ተቋማት አገልግሎት ማግኘት ለሚቸገሩ እና ዝቅተኛ ገቢ ላላቸው የማኅበረሰብ ክፍሎች ተመጣጣኝ የብድርና ቁጠባ አገልግሎት መስጠትን ዋነኛ ተልዕኮው አድርጎ እየተንቀሳቀሰ ይገኛል።
በምረቃው ስነ-ስርዓት ላይ እንደተገለጸው፣ ድሬ ማይክሮ ፋይናንስ በአሁኑ ወቅት አስደናቂ የፋይናንስ አፈጻጸም እያስመዘገበ ነው ተብሏል።
በምረቃውም ስነ ስርዓት ላይ
* ከ1.7 ቢሊየን ብር በላይ የብድር ክምችት
(Total Loan Outstanding) እንዳለው፣
* ከ111 ሺህ በላይ የቁጠባና የብድር ደንበኞችን ማፍራቱን፣
* የተቋሙ አጠቃላይ ካፒታል ከ677 ሚሊየን ብር በላይ መድረሱ ተመላክቷል።
በተለይም በፋይናንስ ተቋማት ውስጥ እንደ ትልቅ ስጋት የሚታየው ለአደጋ የተጋለጠ ብድር (PAR) መጠንን ወደ 0.73% ዝቅ ማድረግ መቻሉ፣ የተቋሙን አስተማማኝነት እና የብድር አሰጣጥ ጥራት የሚያሳይ እንደሆነ ተብራርቷል።
ድሬ ማይክሮ ፋይናንስ ከመደበኛ የብድር እና ቁጠባ አገልግሎት በተጨማሪ፤ የህብረተሰቡን እሴት ያገናዘበ ከወለድ ነፃ የፋይናንስ አገልግሎት፣ የማሽነሪ ሊዝ፣ እንዲሁም እንደ ንጹህ ኢነርጂ (Clean Energy) እና ውሃና ሳኒቴሽን (WASH) ላሉ ዘርፎች የብድር አገልግሎት በመስጠት በፈጠራ ታግዞ እየሰራ እንደሚገኝ ተገልጿል።
አዲሱ የአዲስ አበባ ቅርንጫፍም ፣ ለወጣቶች፣ ለሴቶች እና ለአነስተኛ የንግድ ስራ ፈጣሪዎች የስኬት በር እንደሚሆን በምረቃው ላይ መልዕክት ተላልፏል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #diremicrofinance #financialinclusion #newbranch #addisababa #bolemichael #ethiopia #microfinance #economicempowerment #ድሬማይክሮፋይናንስ #ፋይናንስ #አዲስአበባ
#ethiopia | በምስራቅ ኢትዮጵያ በፋይናንስ ተደራሽነት ላይ ከፍተኛ አሻራ በማሳረፍ የሚታወቀው ድሬ ማይክሮ ፋይናንስ፣ አገልግሎቱን ወደ መዲናዋ አዲስ አበባ በማስፋት የመጀመሪያ የሆነውን የቦሌ ሚካኤል ቅርንጫፍ በዛሬው ዕለት በደማቅ ስነ-ስርዓት አስመረቀ።
ተቋሙ አዲስ አበባን ጨምሮ በድሬዳዋ፣ በሐረር፣ በጅግጅጋ እና በሀሮማያ ከተሞች ተደራሽነቱን በማስፋት፣ ለህብረተሰቡ የፋይናንስ አገልግሎትን በእኩልነት ለማዳረስ እየሰራ መሆኑ በምረቃው ላይ ተገልጿል።
በተለይም በትልልቅ የፋይናንስ ተቋማት አገልግሎት ማግኘት ለሚቸገሩ እና ዝቅተኛ ገቢ ላላቸው የማኅበረሰብ ክፍሎች ተመጣጣኝ የብድርና ቁጠባ አገልግሎት መስጠትን ዋነኛ ተልዕኮው አድርጎ እየተንቀሳቀሰ ይገኛል።
በምረቃው ስነ-ስርዓት ላይ እንደተገለጸው፣ ድሬ ማይክሮ ፋይናንስ በአሁኑ ወቅት አስደናቂ የፋይናንስ አፈጻጸም እያስመዘገበ ነው ተብሏል።
በምረቃውም ስነ ስርዓት ላይ
* ከ1.7 ቢሊየን ብር በላይ የብድር ክምችት
(Total Loan Outstanding) እንዳለው፣
* ከ111 ሺህ በላይ የቁጠባና የብድር ደንበኞችን ማፍራቱን፣
* የተቋሙ አጠቃላይ ካፒታል ከ677 ሚሊየን ብር በላይ መድረሱ ተመላክቷል።
በተለይም በፋይናንስ ተቋማት ውስጥ እንደ ትልቅ ስጋት የሚታየው ለአደጋ የተጋለጠ ብድር (PAR) መጠንን ወደ 0.73% ዝቅ ማድረግ መቻሉ፣ የተቋሙን አስተማማኝነት እና የብድር አሰጣጥ ጥራት የሚያሳይ እንደሆነ ተብራርቷል።
ድሬ ማይክሮ ፋይናንስ ከመደበኛ የብድር እና ቁጠባ አገልግሎት በተጨማሪ፤ የህብረተሰቡን እሴት ያገናዘበ ከወለድ ነፃ የፋይናንስ አገልግሎት፣ የማሽነሪ ሊዝ፣ እንዲሁም እንደ ንጹህ ኢነርጂ (Clean Energy) እና ውሃና ሳኒቴሽን (WASH) ላሉ ዘርፎች የብድር አገልግሎት በመስጠት በፈጠራ ታግዞ እየሰራ እንደሚገኝ ተገልጿል።
አዲሱ የአዲስ አበባ ቅርንጫፍም ፣ ለወጣቶች፣ ለሴቶች እና ለአነስተኛ የንግድ ስራ ፈጣሪዎች የስኬት በር እንደሚሆን በምረቃው ላይ መልዕክት ተላልፏል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #diremicrofinance #financialinclusion #newbranch #addisababa #bolemichael #ethiopia #microfinance #economicempowerment #ድሬማይክሮፋይናንስ #ፋይናንስ #አዲስአበባ