1 month ago
የኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባልነት ሂደት ወደ ሌላ ታላቅ ምዕራፍ ተሻገረ
************************
ኢትዮጵያ ወደ ዓለም የንግድ ድርጅት (WTO) ለመቀላቀል እያደረገች ባለው ታሪካዊ ጉዞ ውስጥ ሌላ ትልቅ እና ስትራቴጂካዊ ስኬት አስመዝግባለች።
ሀገራችን ከኒውዚላንድ ጋር በጄኔቫ በሚገኘው የዓለም የንግድ ድርጅት ዋና መሥሪያ ቤት የሁለትዮሽ የገበያ ተደራሽነት ፕሮቶኮል ተፈራርማለች።
ይህ ስምምነት ኢትዮጵያ የድርጅቱ አባል ለመሆን ለምታደርገው ጥረት እጅግ ወሳኝ ምዕራፍ መሆኑ ተመልክቷል።
ይህንን እጅግ አስፈላጊ ስምምነት በስዊዘርላንድ ጄኔቫ በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት እና በሌሎች ዓለም አቀፍ ድርጅቶች የኢትዮጵያ ቋሚ መልዕክተኛ የሆኑት አምባሳደር ፀጋብ ከበበው እና የኒውዚላንድ የዓለም የንግድ ድርጅት ቋሚ መልዕክተኛ እንዲሁም የድርጅቱ አጠቃላይ ምክር ቤት ሰብሳቢ አምባሳደር ክሌር ኬሊ በጋራ ፈርመውታል።
በፊርማ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ ንግግር ያደረጉት አምባሳደር ፀጋብ ከበበው ስምምነቱ ሁለቱ ሀገራት ያላቸውን የኢኮኖሚ ትብብር ይበልጥ ለማጠናከር እና ግልጽ እንዲሁም በሕግ ላይ የተመሠረተ ሁለገብ የንግድ ሥርዓትን በጋራ ለመደገፍ ያላቸውን ቁርጠኝነት የሚያሳይ መሆኑን ገልጸዋል።
አምባሳደሩ አክለውም የዓለም የንግድ ድርጅት አባል መሆን በኢትዮጵያ አሁን ላይ እየተከናወነ ባለው ሀገራዊ የኢኮኖሚ ማሻሻያ አጀንዳ ውስጥ ስትራቴጂካዊ እና ቀዳሚ ብሔራዊ ትኩረት ሆኖ እንደሚቀጥል በድጋሚ አረጋግጠዋል።
የኒውዚላንድ አምባሳደር ክሌር ኬሊ ኢትዮጵያ ላስመዘገበችው ለዚህ ትልቅ ስኬት የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡
ሀገራቸው ኒውዚላንድ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል እንድትሆን የምታደርገውን ቀጣይነት ያለው ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል በድጋሚ ማረጋገጣቸውን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
በሄዋን ጌታቸው
#ethiopia #ebc #newzealand #wtoaccession #tradeagreement #geneva
************************
ኢትዮጵያ ወደ ዓለም የንግድ ድርጅት (WTO) ለመቀላቀል እያደረገች ባለው ታሪካዊ ጉዞ ውስጥ ሌላ ትልቅ እና ስትራቴጂካዊ ስኬት አስመዝግባለች።
ሀገራችን ከኒውዚላንድ ጋር በጄኔቫ በሚገኘው የዓለም የንግድ ድርጅት ዋና መሥሪያ ቤት የሁለትዮሽ የገበያ ተደራሽነት ፕሮቶኮል ተፈራርማለች።
ይህ ስምምነት ኢትዮጵያ የድርጅቱ አባል ለመሆን ለምታደርገው ጥረት እጅግ ወሳኝ ምዕራፍ መሆኑ ተመልክቷል።
ይህንን እጅግ አስፈላጊ ስምምነት በስዊዘርላንድ ጄኔቫ በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት እና በሌሎች ዓለም አቀፍ ድርጅቶች የኢትዮጵያ ቋሚ መልዕክተኛ የሆኑት አምባሳደር ፀጋብ ከበበው እና የኒውዚላንድ የዓለም የንግድ ድርጅት ቋሚ መልዕክተኛ እንዲሁም የድርጅቱ አጠቃላይ ምክር ቤት ሰብሳቢ አምባሳደር ክሌር ኬሊ በጋራ ፈርመውታል።
በፊርማ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ ንግግር ያደረጉት አምባሳደር ፀጋብ ከበበው ስምምነቱ ሁለቱ ሀገራት ያላቸውን የኢኮኖሚ ትብብር ይበልጥ ለማጠናከር እና ግልጽ እንዲሁም በሕግ ላይ የተመሠረተ ሁለገብ የንግድ ሥርዓትን በጋራ ለመደገፍ ያላቸውን ቁርጠኝነት የሚያሳይ መሆኑን ገልጸዋል።
አምባሳደሩ አክለውም የዓለም የንግድ ድርጅት አባል መሆን በኢትዮጵያ አሁን ላይ እየተከናወነ ባለው ሀገራዊ የኢኮኖሚ ማሻሻያ አጀንዳ ውስጥ ስትራቴጂካዊ እና ቀዳሚ ብሔራዊ ትኩረት ሆኖ እንደሚቀጥል በድጋሚ አረጋግጠዋል።
የኒውዚላንድ አምባሳደር ክሌር ኬሊ ኢትዮጵያ ላስመዘገበችው ለዚህ ትልቅ ስኬት የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡
ሀገራቸው ኒውዚላንድ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል እንድትሆን የምታደርገውን ቀጣይነት ያለው ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል በድጋሚ ማረጋገጣቸውን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
በሄዋን ጌታቸው
#ethiopia #ebc #newzealand #wtoaccession #tradeagreement #geneva
3 months ago
79ኛዉ የዓለም ጤና ጉባኤ በስዊዘርላንድ ጄኔቫ እየተካሄደ ይገኛል #wha79
_____________
በጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ የተመራዉ የኢትዮጵያ ልዑካን ቡድን በጄኔቫ እየተካሄደ በለዉ 79ኛዉ የዓለም ጤና ጉባኤ ላይ እየተሳተፈ ይገኛል።
በጉባኤዉ ላይ ንግግር ያደረጉት የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ በቅርቡ ይፋ የሆነዉ የህብረተሰብ ጤና ዳሰሳ ጥናት ግኝት መሰረት ኢትዮጵያ የእናቶችና ህጻናት ሞትን በመቀነስ ረገድ አመርቂ ዉጤት ማስመዝገቧን በመግለጽ በቀጣይም አለም አቀፍ የጤና ተደራሽነትን በማረጋገጥ ለመጀመሪያ ደረጃ ጤና ክብካቤ ከፍተኛ ትኩረት ተሰጥቶ ጠንካራ የጤና ስርዓት እንዲፈጠር በትጋት እንደሚሰራ አጽንኦት በመስጠት ተናግረዋል።
በመላዉ ህብረተሰብ ተሳትፎና የሚመለከታቸዉ ባለድርሻ አካላት ቅንጅት እንዲሁም የጤና ባለሙያዉን ተነሳሽነትና ተጠቃሚነት በማረጋገጥ የእናቶችና ህጸናት ጤናን በቀጣይነት ማሻሻል፣ ተላላፊና ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎችን መከላከልና መቆጣጠር፣ በዘመናዊ ቴክኖሎጂ በመታገዝ ጥራት ያለዉ የጤና አገልግሎት ተደራሽ እንዲሆን በትኩረት እንደሚሰራ የገለጹት ሚኒስትሯ ኢትዮጵያ ቀጣይነት ያለዉ የጤና ልማት ግቦችን ለማሳካት ከዓለም ጤና ድርጅት፣ ከአፍርካ ህብረት፣ ከሀገራት፣ ከሀገር በቀልና አለም አቀፍ አጋር ድርጅቶች እንዲሁም ሁሉም ባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት ለመስራት ቁርጠኛ መሆኗን ገልጸዋል።
The 79th World Health Assembly is being held in Geneva, Switzerland
______________
The Ethiopian delegation led by Health Minister Dr. Mekdes Daba is participating in the 79th World Health Assembly being held in Geneva.
Health Minister Dr. Mekdes Daba, who made a speech at the assembly, stated that according to the recently released public health survey findings, Ethiopia has recorded encouraging results in reducing maternal and child mortality, and emphasized that in the future, by ensuring universal health coverage, high attention will be given to primary health care to diligently work towards creating a strong health system.
The Minister stated that focus will be given to continuously improving maternal and child health through the participation of the entire community and the coordination of relevant stakeholders, as well as by ensuring the motivation and benefit of health professionals, and preventing and controlling communicable and non-communicable diseases, and making quality health services accessible with the help of modern technology: also expressed that Ethiopia is committed to working in coordination with the World Health Organization, the African Union, countries, local and international partner organizations, as well as all stakeholders to achieve the sustainable health development goals.
_____________
በጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ የተመራዉ የኢትዮጵያ ልዑካን ቡድን በጄኔቫ እየተካሄደ በለዉ 79ኛዉ የዓለም ጤና ጉባኤ ላይ እየተሳተፈ ይገኛል።
በጉባኤዉ ላይ ንግግር ያደረጉት የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ በቅርቡ ይፋ የሆነዉ የህብረተሰብ ጤና ዳሰሳ ጥናት ግኝት መሰረት ኢትዮጵያ የእናቶችና ህጻናት ሞትን በመቀነስ ረገድ አመርቂ ዉጤት ማስመዝገቧን በመግለጽ በቀጣይም አለም አቀፍ የጤና ተደራሽነትን በማረጋገጥ ለመጀመሪያ ደረጃ ጤና ክብካቤ ከፍተኛ ትኩረት ተሰጥቶ ጠንካራ የጤና ስርዓት እንዲፈጠር በትጋት እንደሚሰራ አጽንኦት በመስጠት ተናግረዋል።
በመላዉ ህብረተሰብ ተሳትፎና የሚመለከታቸዉ ባለድርሻ አካላት ቅንጅት እንዲሁም የጤና ባለሙያዉን ተነሳሽነትና ተጠቃሚነት በማረጋገጥ የእናቶችና ህጸናት ጤናን በቀጣይነት ማሻሻል፣ ተላላፊና ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎችን መከላከልና መቆጣጠር፣ በዘመናዊ ቴክኖሎጂ በመታገዝ ጥራት ያለዉ የጤና አገልግሎት ተደራሽ እንዲሆን በትኩረት እንደሚሰራ የገለጹት ሚኒስትሯ ኢትዮጵያ ቀጣይነት ያለዉ የጤና ልማት ግቦችን ለማሳካት ከዓለም ጤና ድርጅት፣ ከአፍርካ ህብረት፣ ከሀገራት፣ ከሀገር በቀልና አለም አቀፍ አጋር ድርጅቶች እንዲሁም ሁሉም ባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት ለመስራት ቁርጠኛ መሆኗን ገልጸዋል።
The 79th World Health Assembly is being held in Geneva, Switzerland
______________
The Ethiopian delegation led by Health Minister Dr. Mekdes Daba is participating in the 79th World Health Assembly being held in Geneva.
Health Minister Dr. Mekdes Daba, who made a speech at the assembly, stated that according to the recently released public health survey findings, Ethiopia has recorded encouraging results in reducing maternal and child mortality, and emphasized that in the future, by ensuring universal health coverage, high attention will be given to primary health care to diligently work towards creating a strong health system.
The Minister stated that focus will be given to continuously improving maternal and child health through the participation of the entire community and the coordination of relevant stakeholders, as well as by ensuring the motivation and benefit of health professionals, and preventing and controlling communicable and non-communicable diseases, and making quality health services accessible with the help of modern technology: also expressed that Ethiopia is committed to working in coordination with the World Health Organization, the African Union, countries, local and international partner organizations, as well as all stakeholders to achieve the sustainable health development goals.
3 months ago
ኢትዮጵያ እንደ ዓለም ጤና ጉባኤ ያሉ አለም አቀፍ መድረኮችን በመጠቀም የጤና ዲፕሎማሲን በማጠናከር ላይ ትገኛለች - የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ
በጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ የተመራዉ የኢትዮጵያ ልዑክ ቡድን በ79 ነኛዉ የዓለም ጤና ጉባኤ ላይ ለመሳተፍ ስዊዘርላንድ ጄኔቫ ገብቷል።
ዶ/ር መቅደስ ለልዑካን ቡድኑ ኦሪየንቴሽን በሰጡት መድረክ እንደገለጹት ኢትዮጵያ በተለይም እንደ የዓለም ጤና ጉባኤ ያሉ አለም አቀፍ መድረኮችን በመጠቀም የጤና ዲፕሎማሲን በማጠናከር ላይ ትገኛለች ብለዋል።
ኢትዮጵያ የዓለም ጤና ድርጅት አባል ሀገር እንደመሆኗ በጉባኤዉ በሚወሰኑ ዉሳኔዎችና ቀጣይ ስራዎች የራሷን ድርሻ እንደምትወጣ ዶ/ር መቅደስ ተናግረዋል።
ወቅታዊ የኢቦላና ሀንታ ቫይረስ ሁኔታን ጨምሮ ሌሎች የዓለማችን ስጋት የሆኑ ወርሽኞችን መከላከልና መቆጣጠር በዋናነት በጉባኤዉ ቀርበዉ ዉይይት እንደሚደረግበት ይጠበቃል።
ከጉኤዉ ቀደም ብለዉ የዎክ ዘ ቶክ (Walk the Talk) ፕሮግራም የተካሄደ ሲሆን 79 ነኛው የዓለም ጤና ጉባኤ ከግንቦት 10-15 /2018 ዓ.ም በስዊዘርላድ ጄኔቫ እንደሚካሄድ ከወጣዉ ፕሮግራም ማወቅ ተችሏል።
"Ethiopia is strengthening health diplomacy by using international forums such as the World Health Assembly" - Health Minister Dr. Mekdes Daba
____________
The Ethiopian delegation led by Health Minister Dr. Mekdes Daba has arrived in Geneva, Switzerland to participate in the 79th World Health Assembly.
Dr. Mekdes, during the orientation forum she gave to the delegation, stated that Ethiopia is strengthening health diplomacy particularly by using international forums such as the World Health Assembly.
Dr. Mekdes said that as Ethiopia is a member state of the World Health Organization, it will play its own role in the decisions and future works to be decided at the assembly.
Preventing and controlling other world-threatening pandemics, including the current Ebola and Hanta virus situation, is mainly expected to be presented and discussed at the assembly.
Prior to the assembly, the Walk the Talk program was held, and it was possible to know from the released program that the 79th World Health Assembly will be held from May 18-23 / 2026 in Geneva, Switzerland.
በጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ የተመራዉ የኢትዮጵያ ልዑክ ቡድን በ79 ነኛዉ የዓለም ጤና ጉባኤ ላይ ለመሳተፍ ስዊዘርላንድ ጄኔቫ ገብቷል።
ዶ/ር መቅደስ ለልዑካን ቡድኑ ኦሪየንቴሽን በሰጡት መድረክ እንደገለጹት ኢትዮጵያ በተለይም እንደ የዓለም ጤና ጉባኤ ያሉ አለም አቀፍ መድረኮችን በመጠቀም የጤና ዲፕሎማሲን በማጠናከር ላይ ትገኛለች ብለዋል።
ኢትዮጵያ የዓለም ጤና ድርጅት አባል ሀገር እንደመሆኗ በጉባኤዉ በሚወሰኑ ዉሳኔዎችና ቀጣይ ስራዎች የራሷን ድርሻ እንደምትወጣ ዶ/ር መቅደስ ተናግረዋል።
ወቅታዊ የኢቦላና ሀንታ ቫይረስ ሁኔታን ጨምሮ ሌሎች የዓለማችን ስጋት የሆኑ ወርሽኞችን መከላከልና መቆጣጠር በዋናነት በጉባኤዉ ቀርበዉ ዉይይት እንደሚደረግበት ይጠበቃል።
ከጉኤዉ ቀደም ብለዉ የዎክ ዘ ቶክ (Walk the Talk) ፕሮግራም የተካሄደ ሲሆን 79 ነኛው የዓለም ጤና ጉባኤ ከግንቦት 10-15 /2018 ዓ.ም በስዊዘርላድ ጄኔቫ እንደሚካሄድ ከወጣዉ ፕሮግራም ማወቅ ተችሏል።
"Ethiopia is strengthening health diplomacy by using international forums such as the World Health Assembly" - Health Minister Dr. Mekdes Daba
____________
The Ethiopian delegation led by Health Minister Dr. Mekdes Daba has arrived in Geneva, Switzerland to participate in the 79th World Health Assembly.
Dr. Mekdes, during the orientation forum she gave to the delegation, stated that Ethiopia is strengthening health diplomacy particularly by using international forums such as the World Health Assembly.
Dr. Mekdes said that as Ethiopia is a member state of the World Health Organization, it will play its own role in the decisions and future works to be decided at the assembly.
Preventing and controlling other world-threatening pandemics, including the current Ebola and Hanta virus situation, is mainly expected to be presented and discussed at the assembly.
Prior to the assembly, the Walk the Talk program was held, and it was possible to know from the released program that the 79th World Health Assembly will be held from May 18-23 / 2026 in Geneva, Switzerland.
3 months ago
የኢትዮጵያ አየር መንገድ
የኢትዮጵያ የዲፕሎማሲና የኢኮኖሚ ጥንካሬ መገለጫ
#ethiopia | የኢትዮጵያ አየር መንገድ ባለፉት ሰባ ዓመታት ከተራ የንግድ ተቋምነት ባለፈ፣ የሀገሪቱን የውጭ ግንኙነት ፖሊሲ የሚያስፈጽም ቀዳሚ የዲፕሎማሲ መሣሪያ ሆኖ አገልግሏል።
ተቋሙ በተለይ የኢትዮጵያን "Soft Power" ወይም ለስላሳ ኃይል በዓለም መድረክ ላይ በማገንነን ረገድ ወደር የለውም።
፩. የፓን-አፍሪካኒዝም ክንፍ
(The Wing of Pan-Africanism)
አየር መንገዱ አፍሪካን እርስ በእርስ በማገናኘት የፓን-አፍሪካኒዝም ርዕዮትን በተግባር ቀይሮታል። ብዙ የአህጉሪቱ ሀገራት የራሳቸው አየር መንገድ በሌላቸው ወቅት፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ክፍተቱን በመሙላት የኢትዮጵያን ስልታዊ ተሰሚነት (Strategic Importance) ከፍ አድርጎታል።
ዛሬም ለ"አፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጠና" (AfCFTA) ስኬት ዋነኛው የሎጂስቲክስ ሞተር ሆኖ እያገለገለ ይገኛል።
፪. ሰብዓዊ ዲፕሎማሲ
(Humanitarian Diplomacy)
የኮቪድ-19 ትዝታ
አብዛኞቹ ዓለም አቀፍ አየር መንገዶች በረራ ባቆሙበት ወቅት፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የሕክምና ቁሳቁሶችን በማጓጓዝ እንደ ዓለም አቀፍ የሎጂስቲክስ ማዕከል ሆኖ አገልግሏል።
የኢቦላ ወረርሽኝ
በ2014 በምዕራብ አፍሪካ ወረርሽኙ በተከሰተ ጊዜ በረራ ባለማቋረጥ 'የችግር ጊዜ አጋር' መሆኑን በተግባር አሳይቷል። ይህ የሀገራችንን በጎ ገጽታ በዓለም ፊት ገንብቶታል።
፫. አዲስ አበባ፦ "የአፍሪካ ጄኔቫ"
(The Geneva of Africa)
አዲስ አበባ የአፍሪካ ኅብረት (AU) እና የተመድ የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን መቀመጫ እንድትሆን ካስቻሏት ዋና ዋና ምክንያቶች አንዱ የአየር መንገዱ ሰፊ መዳረሻ ነው።
መሪዎችና ዲፕሎማቶች በቀላሉ ወደ አዲስ አበባ እንዲመጡ በማድረግ ከተማዋ የአህጉሪቱ ፖለቲካዊ ርዕሰ መዲና ሆና እንድትቀጥል አድርጓል።
፬. የአሜሪካና ቦይንግ ቁርኝት
(The Boeing Factor)
አየር መንገዱ ከአሜሪካው ቦይንግ ኩባንያ ጋር ያለው የረጅም ዘመን ግንኙነት ለኢኮኖሚ ዲፕሎማሲያችን እንደ ምሶሶ ይቆጠራል።
ስትራቴጂካዊ አጋርነት
ኢትዮጵያ በአሜሪካ እይታ የዕርዳታ ፈላጊነት ገጽታዋ ተቀይሮ 'ስትራቴጂካዊ የንግድ አጋር' እንድትሆን አድርጓታል።
የፖለቲካ ማለስለሻ
(Lobbying Power)
በሁለቱ ሀገራት መካከል የፖለቲካ አለመግባባቶች በሚፈጠሩበት ወቅት እንኳን፣ እንደ ቦይንግ ያሉ ግዙፍ ተቋማት የንግድ ፍላጎት ግንኙነቱ እንዳይላላ እንደ ዋስትና ሆኖ ያገለግላል።
የ737 MAX ቀውስ
አየር መንገዱ አደጋውን ያስተዳደረበት ሙያዊ ብቃት፣ በዓለም አቀፍ የአቪዬሽን ማህበረሰብ ዘንድ 'አስተማማኝ አጋር' የሚል የከበረ ስም አሰጥቶታል።
ባጭሩ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ቦይንግን መምረጡ የቴክኖሎጂ ፍላጎት ብቻ ሳይሆን፣ ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ ፖለቲካ ውስጥ ልዩ ስፍራ እንድታገኝ የሚያስችል ብልኅ የኢኮኖሚ ዲፕሎማሲ መሣሪያ ነው። ይህ ተቋም የሀገራችን ኩራት ብቻ ሳይሆን የዲፕሎማሲያችን ጋሻም ነው።
ለ Getu Tenesgen ( ጌጡ ተመስገን )
ቀመርቲ ጨንገሬ
#ethiopianairlines #diplomacy #boeing #panafricanism #aviation #economy #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa #softpower #ethiopia
የኢትዮጵያ የዲፕሎማሲና የኢኮኖሚ ጥንካሬ መገለጫ
#ethiopia | የኢትዮጵያ አየር መንገድ ባለፉት ሰባ ዓመታት ከተራ የንግድ ተቋምነት ባለፈ፣ የሀገሪቱን የውጭ ግንኙነት ፖሊሲ የሚያስፈጽም ቀዳሚ የዲፕሎማሲ መሣሪያ ሆኖ አገልግሏል።
ተቋሙ በተለይ የኢትዮጵያን "Soft Power" ወይም ለስላሳ ኃይል በዓለም መድረክ ላይ በማገንነን ረገድ ወደር የለውም።
፩. የፓን-አፍሪካኒዝም ክንፍ
(The Wing of Pan-Africanism)
አየር መንገዱ አፍሪካን እርስ በእርስ በማገናኘት የፓን-አፍሪካኒዝም ርዕዮትን በተግባር ቀይሮታል። ብዙ የአህጉሪቱ ሀገራት የራሳቸው አየር መንገድ በሌላቸው ወቅት፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ክፍተቱን በመሙላት የኢትዮጵያን ስልታዊ ተሰሚነት (Strategic Importance) ከፍ አድርጎታል።
ዛሬም ለ"አፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጠና" (AfCFTA) ስኬት ዋነኛው የሎጂስቲክስ ሞተር ሆኖ እያገለገለ ይገኛል።
፪. ሰብዓዊ ዲፕሎማሲ
(Humanitarian Diplomacy)
የኮቪድ-19 ትዝታ
አብዛኞቹ ዓለም አቀፍ አየር መንገዶች በረራ ባቆሙበት ወቅት፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የሕክምና ቁሳቁሶችን በማጓጓዝ እንደ ዓለም አቀፍ የሎጂስቲክስ ማዕከል ሆኖ አገልግሏል።
የኢቦላ ወረርሽኝ
በ2014 በምዕራብ አፍሪካ ወረርሽኙ በተከሰተ ጊዜ በረራ ባለማቋረጥ 'የችግር ጊዜ አጋር' መሆኑን በተግባር አሳይቷል። ይህ የሀገራችንን በጎ ገጽታ በዓለም ፊት ገንብቶታል።
፫. አዲስ አበባ፦ "የአፍሪካ ጄኔቫ"
(The Geneva of Africa)
አዲስ አበባ የአፍሪካ ኅብረት (AU) እና የተመድ የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን መቀመጫ እንድትሆን ካስቻሏት ዋና ዋና ምክንያቶች አንዱ የአየር መንገዱ ሰፊ መዳረሻ ነው።
መሪዎችና ዲፕሎማቶች በቀላሉ ወደ አዲስ አበባ እንዲመጡ በማድረግ ከተማዋ የአህጉሪቱ ፖለቲካዊ ርዕሰ መዲና ሆና እንድትቀጥል አድርጓል።
፬. የአሜሪካና ቦይንግ ቁርኝት
(The Boeing Factor)
አየር መንገዱ ከአሜሪካው ቦይንግ ኩባንያ ጋር ያለው የረጅም ዘመን ግንኙነት ለኢኮኖሚ ዲፕሎማሲያችን እንደ ምሶሶ ይቆጠራል።
ስትራቴጂካዊ አጋርነት
ኢትዮጵያ በአሜሪካ እይታ የዕርዳታ ፈላጊነት ገጽታዋ ተቀይሮ 'ስትራቴጂካዊ የንግድ አጋር' እንድትሆን አድርጓታል።
የፖለቲካ ማለስለሻ
(Lobbying Power)
በሁለቱ ሀገራት መካከል የፖለቲካ አለመግባባቶች በሚፈጠሩበት ወቅት እንኳን፣ እንደ ቦይንግ ያሉ ግዙፍ ተቋማት የንግድ ፍላጎት ግንኙነቱ እንዳይላላ እንደ ዋስትና ሆኖ ያገለግላል።
የ737 MAX ቀውስ
አየር መንገዱ አደጋውን ያስተዳደረበት ሙያዊ ብቃት፣ በዓለም አቀፍ የአቪዬሽን ማህበረሰብ ዘንድ 'አስተማማኝ አጋር' የሚል የከበረ ስም አሰጥቶታል።
ባጭሩ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ቦይንግን መምረጡ የቴክኖሎጂ ፍላጎት ብቻ ሳይሆን፣ ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ ፖለቲካ ውስጥ ልዩ ስፍራ እንድታገኝ የሚያስችል ብልኅ የኢኮኖሚ ዲፕሎማሲ መሣሪያ ነው። ይህ ተቋም የሀገራችን ኩራት ብቻ ሳይሆን የዲፕሎማሲያችን ጋሻም ነው።
ለ Getu Tenesgen ( ጌጡ ተመስገን )
ቀመርቲ ጨንገሬ
#ethiopianairlines #diplomacy #boeing #panafricanism #aviation #economy #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa #softpower #ethiopia
Sponsored by
Surafel
4 months ago
"አቅማችን ተሟጧል!"
— ኢትዮጵያ ለዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ አስቸኳይ ጥሪ አቀረበች
#ethiopia | ኢትዮጵያ ወደ አገሪቱ የሚገቡ ስደተኞች ቁጥር በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ በመምጣቱ፣ መሠረታዊ አገልግሎቶችን ለማቅረብ የመንግስት አቅም እየተሟጠጠ መሆኑን በይፋ አስታወቀች።
በተለይ በትምህርትና በጤና ዘርፍ የሚሰጡ አገልግሎቶች በስደተኞች ቁጥር መጨመር ምክንያት ከፍተኛ ጫና ወድቆባቸዋል።
በጄኔቫ የኢትዮጵያ ቋሚ መልዕክተኛ አምባሳደር ጸጋዓብ ክበበው በተመድ ስደተኞች ኮሚሽን ስብሰባ ላይ የሀገሪቱን ስጋት በዝርዝር አቅርበዋል።
ዓለማቀፉ ማኅበረሰብ ዘላቂ የገንዘብ ድጋፍ እንዲያደርግ እና ስደተኞች በሚገኙባቸው አካባቢዎች በኢንቨስትመንት እንዲሳተፍ ተጠይቋል።
ከገንዘብ ድጋፍ ባለፈ፣ ለስደቱ መሠረት የሆኑ ችግሮችን በመፍታት ረገድ ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ንቁ ተሳትፎ እንዲያደርግ አምባሳደሩ አሳስበዋል።
#ethiopia #refugees #humanitarianaid #unhcr #geneva #addisadmas #breakingnews #globalcall #ኢትዮጵያ #ስደተኞች
— ኢትዮጵያ ለዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ አስቸኳይ ጥሪ አቀረበች
#ethiopia | ኢትዮጵያ ወደ አገሪቱ የሚገቡ ስደተኞች ቁጥር በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ በመምጣቱ፣ መሠረታዊ አገልግሎቶችን ለማቅረብ የመንግስት አቅም እየተሟጠጠ መሆኑን በይፋ አስታወቀች።
በተለይ በትምህርትና በጤና ዘርፍ የሚሰጡ አገልግሎቶች በስደተኞች ቁጥር መጨመር ምክንያት ከፍተኛ ጫና ወድቆባቸዋል።
በጄኔቫ የኢትዮጵያ ቋሚ መልዕክተኛ አምባሳደር ጸጋዓብ ክበበው በተመድ ስደተኞች ኮሚሽን ስብሰባ ላይ የሀገሪቱን ስጋት በዝርዝር አቅርበዋል።
ዓለማቀፉ ማኅበረሰብ ዘላቂ የገንዘብ ድጋፍ እንዲያደርግ እና ስደተኞች በሚገኙባቸው አካባቢዎች በኢንቨስትመንት እንዲሳተፍ ተጠይቋል።
ከገንዘብ ድጋፍ ባለፈ፣ ለስደቱ መሠረት የሆኑ ችግሮችን በመፍታት ረገድ ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ንቁ ተሳትፎ እንዲያደርግ አምባሳደሩ አሳስበዋል።
#ethiopia #refugees #humanitarianaid #unhcr #geneva #addisadmas #breakingnews #globalcall #ኢትዮጵያ #ስደተኞች
Comments