1 month ago
የኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባልነት ሂደት ወደ ሌላ ታላቅ ምዕራፍ ተሻገረ
************************
ኢትዮጵያ ወደ ዓለም የንግድ ድርጅት (WTO) ለመቀላቀል እያደረገች ባለው ታሪካዊ ጉዞ ውስጥ ሌላ ትልቅ እና ስትራቴጂካዊ ስኬት አስመዝግባለች።
ሀገራችን ከኒውዚላንድ ጋር በጄኔቫ በሚገኘው የዓለም የንግድ ድርጅት ዋና መሥሪያ ቤት የሁለትዮሽ የገበያ ተደራሽነት ፕሮቶኮል ተፈራርማለች።
ይህ ስምምነት ኢትዮጵያ የድርጅቱ አባል ለመሆን ለምታደርገው ጥረት እጅግ ወሳኝ ምዕራፍ መሆኑ ተመልክቷል።
ይህንን እጅግ አስፈላጊ ስምምነት በስዊዘርላንድ ጄኔቫ በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት እና በሌሎች ዓለም አቀፍ ድርጅቶች የኢትዮጵያ ቋሚ መልዕክተኛ የሆኑት አምባሳደር ፀጋብ ከበበው እና የኒውዚላንድ የዓለም የንግድ ድርጅት ቋሚ መልዕክተኛ እንዲሁም የድርጅቱ አጠቃላይ ምክር ቤት ሰብሳቢ አምባሳደር ክሌር ኬሊ በጋራ ፈርመውታል።
በፊርማ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ ንግግር ያደረጉት አምባሳደር ፀጋብ ከበበው ስምምነቱ ሁለቱ ሀገራት ያላቸውን የኢኮኖሚ ትብብር ይበልጥ ለማጠናከር እና ግልጽ እንዲሁም በሕግ ላይ የተመሠረተ ሁለገብ የንግድ ሥርዓትን በጋራ ለመደገፍ ያላቸውን ቁርጠኝነት የሚያሳይ መሆኑን ገልጸዋል።
አምባሳደሩ አክለውም የዓለም የንግድ ድርጅት አባል መሆን በኢትዮጵያ አሁን ላይ እየተከናወነ ባለው ሀገራዊ የኢኮኖሚ ማሻሻያ አጀንዳ ውስጥ ስትራቴጂካዊ እና ቀዳሚ ብሔራዊ ትኩረት ሆኖ እንደሚቀጥል በድጋሚ አረጋግጠዋል።
የኒውዚላንድ አምባሳደር ክሌር ኬሊ ኢትዮጵያ ላስመዘገበችው ለዚህ ትልቅ ስኬት የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡
ሀገራቸው ኒውዚላንድ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል እንድትሆን የምታደርገውን ቀጣይነት ያለው ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል በድጋሚ ማረጋገጣቸውን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
በሄዋን ጌታቸው
#ethiopia #ebc #newzealand #wtoaccession #tradeagreement #geneva
************************
ኢትዮጵያ ወደ ዓለም የንግድ ድርጅት (WTO) ለመቀላቀል እያደረገች ባለው ታሪካዊ ጉዞ ውስጥ ሌላ ትልቅ እና ስትራቴጂካዊ ስኬት አስመዝግባለች።
ሀገራችን ከኒውዚላንድ ጋር በጄኔቫ በሚገኘው የዓለም የንግድ ድርጅት ዋና መሥሪያ ቤት የሁለትዮሽ የገበያ ተደራሽነት ፕሮቶኮል ተፈራርማለች።
ይህ ስምምነት ኢትዮጵያ የድርጅቱ አባል ለመሆን ለምታደርገው ጥረት እጅግ ወሳኝ ምዕራፍ መሆኑ ተመልክቷል።
ይህንን እጅግ አስፈላጊ ስምምነት በስዊዘርላንድ ጄኔቫ በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት እና በሌሎች ዓለም አቀፍ ድርጅቶች የኢትዮጵያ ቋሚ መልዕክተኛ የሆኑት አምባሳደር ፀጋብ ከበበው እና የኒውዚላንድ የዓለም የንግድ ድርጅት ቋሚ መልዕክተኛ እንዲሁም የድርጅቱ አጠቃላይ ምክር ቤት ሰብሳቢ አምባሳደር ክሌር ኬሊ በጋራ ፈርመውታል።
በፊርማ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ ንግግር ያደረጉት አምባሳደር ፀጋብ ከበበው ስምምነቱ ሁለቱ ሀገራት ያላቸውን የኢኮኖሚ ትብብር ይበልጥ ለማጠናከር እና ግልጽ እንዲሁም በሕግ ላይ የተመሠረተ ሁለገብ የንግድ ሥርዓትን በጋራ ለመደገፍ ያላቸውን ቁርጠኝነት የሚያሳይ መሆኑን ገልጸዋል።
አምባሳደሩ አክለውም የዓለም የንግድ ድርጅት አባል መሆን በኢትዮጵያ አሁን ላይ እየተከናወነ ባለው ሀገራዊ የኢኮኖሚ ማሻሻያ አጀንዳ ውስጥ ስትራቴጂካዊ እና ቀዳሚ ብሔራዊ ትኩረት ሆኖ እንደሚቀጥል በድጋሚ አረጋግጠዋል።
የኒውዚላንድ አምባሳደር ክሌር ኬሊ ኢትዮጵያ ላስመዘገበችው ለዚህ ትልቅ ስኬት የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡
ሀገራቸው ኒውዚላንድ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል እንድትሆን የምታደርገውን ቀጣይነት ያለው ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል በድጋሚ ማረጋገጣቸውን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
በሄዋን ጌታቸው
#ethiopia #ebc #newzealand #wtoaccession #tradeagreement #geneva
6 months ago
"ከኢትዮጵያ ጋር አዲስ የትራንዚትና ትራንስፖርት ስምምነት ለማድረግ እየተነጋገርን ነው" — ፕሬዚዳንት አብዱራህማን አብዱላሂ
#ethiopia | የሶማሊላንዱ ፕሬዚዳንት አብዱራህማን መሐመድ አብዱላሂ ሀገራቸው ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን የኢኮኖሚ ትብብር ወደ ላቀ ደረጃ የሚያሸጋግር አዲስ የትራንዚት ንግድና የትራንስፖርት ስምምነት ለማድረግ በንግግር ላይ መሆናቸውን ገለጹ። ፕሬዚዳንቱ ከሲኤንኤን ቢዝነስ (CNN Business) ጋር በነበራቸው ቆይታ፣ ይህ ስምምነት በቅርቡ ይጠናቀቃል ተብሎ እንደሚጠበቅም ጠቁመዋል።
ፕሬዚዳንቱ በንግግራቸው ያነሷቸው ዋና ዋና ነጥቦች፦
* የኢንቨስትመንት መነቃቃት፦ ሶማሊላንድ ሰላማዊና ዲሞክራሲያዊት ሀገር መሆኗን የገለጹት ፕሬዚዳንቱ፣ ከእስራኤል ያገኙት እውቅና የውጭ ኢንቨስትመንትን ለመሳብ ትልቅ በር እንደሚከፍት ገልጸዋል።
* የበርበራ ኮሪደር እና ኢትዮጵያ፦ የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች የበርበራ ወደብን ከኢትዮጵያ ጋር የሚያገናኘውን ኮሪደር በመገንባት ረገድ ያላትን ድርሻ አውስተው፣ ከኢትዮጵያ የመጣው የመጀመሪያው ዓለም አቀፍ ባንክ በሀገሪቱ የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴ ላይ ያለውን ሚና አድንቀዋል።
* የነዳጅ እና ማዕድን ሀብት፦ ሶማሊላንድ በቢሊዮን የሚቆጠር በርሜል የነዳጅ ሀብት እንዳላትና በ2027 ማውጣት እንደምትጀምር የገለጹት ፕሬዚዳንቱ፣ ከወሳኝ ማዕድናት ጋር በተያያዘም ከአሜሪካ ጋር እየሰሩ መሆኑን ጠቁመዋል።
* ለኢንቨስተሮች የቀረበ ጥሪ፦ በሀገሪቱ ፋብሪካ ለሚገነቡ ኢንቨስተሮች ነፃ መሬትና የረጅም ጊዜ የታክስ እረፍት እንደሚሰጥም ቃል ገብተዋል።
በሌላ በኩል፣ የሶማሊያው ፕሬዚዳንት ሀሰን ሼህ መሐሙድ እስራኤል ለሶማሊላንድ የሰጠችውን እውቅና ለመቀልበስ ከሳዑዲ አረቢያ ጋር እንደሚሰሩ መግለጻቸው የሚታወስ ሲሆን፣ ቀጣናዊው ፖለቲካዊ ውጥረት በንግድ ግንኙነቱ ላይ የሚኖረው ተጽዕኖ የብዙዎች መነጋገሪያ ሆኗል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #ኢትዮጵያ #ሶማሊላንድ #ንግድ #ኢንቨስትመንት #በርበራ #ቀይባህር #somaliland #ethiopia #tradeagreement #hornof Africa #economy
#ethiopia | የሶማሊላንዱ ፕሬዚዳንት አብዱራህማን መሐመድ አብዱላሂ ሀገራቸው ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን የኢኮኖሚ ትብብር ወደ ላቀ ደረጃ የሚያሸጋግር አዲስ የትራንዚት ንግድና የትራንስፖርት ስምምነት ለማድረግ በንግግር ላይ መሆናቸውን ገለጹ። ፕሬዚዳንቱ ከሲኤንኤን ቢዝነስ (CNN Business) ጋር በነበራቸው ቆይታ፣ ይህ ስምምነት በቅርቡ ይጠናቀቃል ተብሎ እንደሚጠበቅም ጠቁመዋል።
ፕሬዚዳንቱ በንግግራቸው ያነሷቸው ዋና ዋና ነጥቦች፦
* የኢንቨስትመንት መነቃቃት፦ ሶማሊላንድ ሰላማዊና ዲሞክራሲያዊት ሀገር መሆኗን የገለጹት ፕሬዚዳንቱ፣ ከእስራኤል ያገኙት እውቅና የውጭ ኢንቨስትመንትን ለመሳብ ትልቅ በር እንደሚከፍት ገልጸዋል።
* የበርበራ ኮሪደር እና ኢትዮጵያ፦ የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች የበርበራ ወደብን ከኢትዮጵያ ጋር የሚያገናኘውን ኮሪደር በመገንባት ረገድ ያላትን ድርሻ አውስተው፣ ከኢትዮጵያ የመጣው የመጀመሪያው ዓለም አቀፍ ባንክ በሀገሪቱ የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴ ላይ ያለውን ሚና አድንቀዋል።
* የነዳጅ እና ማዕድን ሀብት፦ ሶማሊላንድ በቢሊዮን የሚቆጠር በርሜል የነዳጅ ሀብት እንዳላትና በ2027 ማውጣት እንደምትጀምር የገለጹት ፕሬዚዳንቱ፣ ከወሳኝ ማዕድናት ጋር በተያያዘም ከአሜሪካ ጋር እየሰሩ መሆኑን ጠቁመዋል።
* ለኢንቨስተሮች የቀረበ ጥሪ፦ በሀገሪቱ ፋብሪካ ለሚገነቡ ኢንቨስተሮች ነፃ መሬትና የረጅም ጊዜ የታክስ እረፍት እንደሚሰጥም ቃል ገብተዋል።
በሌላ በኩል፣ የሶማሊያው ፕሬዚዳንት ሀሰን ሼህ መሐሙድ እስራኤል ለሶማሊላንድ የሰጠችውን እውቅና ለመቀልበስ ከሳዑዲ አረቢያ ጋር እንደሚሰሩ መግለጻቸው የሚታወስ ሲሆን፣ ቀጣናዊው ፖለቲካዊ ውጥረት በንግድ ግንኙነቱ ላይ የሚኖረው ተጽዕኖ የብዙዎች መነጋገሪያ ሆኗል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #ኢትዮጵያ #ሶማሊላንድ #ንግድ #ኢንቨስትመንት #በርበራ #ቀይባህር #somaliland #ethiopia #tradeagreement #hornof Africa #economy
Comments