3 months ago
ሩሲያ የድል ቀኗን ምክንያት በማድረግ የሁለት ቀናት የተኩስ አቁም አወጀች
*****************
የሩሲያ መከላከያ ሚኒስቴር የሁለተኛው የዓለም ጦርነት መጠናቀቁ የሚዘከርበትን የድል ቀን ምክንያት በማድረግ ለሁለት ቀናት የሚቆይ የተኩስ አቁም ማወጁን አስታውቋል።
ሚኒስቴሩ ዩክሬንም ይህንኑ የተኩስ አቁም ውሳኔ እንድትከተል ጥሪ ያቀረበ ሲሆን፣ በበዓሉ አከባበር ወቅት በሩሲያ ላይ የሚሰነዘር ማንኛውም ጥቃት ካለ የሚሰጠው የአጸፋ መልስ እጅግ ከባድ እንደሚሆን አስጠንቅቋል።
ይህ መግለጫ የወጣው የዩክሬኑ ፕሬዝዳንት ቮሎዲሚር ዘለንስኪ በሞስኮ ቀይ አደባባይ የሚካሄደውን የድል ቀን ሰልፍ ኪየቭ ኢላማ ልታደርግ እንደምትችል መጠቆማቸውን ተከትሎ መሆኑ ተገልጿል።
የሩሲያ ማስጠንቀቂያም በበዓሉ ላይ ማንኛውንም ዓይነት ችግር ለመፍጠር የሚደረጉ ሙከራዎችን ለመከላከል ያለመ መሆኑ ተመላክቷል።
በቢታኒያ ሲሳይ
#russia #ukraine #victoryday #ceasefire #moscow #zelensky #internationalnews #ethiopia
*****************
የሩሲያ መከላከያ ሚኒስቴር የሁለተኛው የዓለም ጦርነት መጠናቀቁ የሚዘከርበትን የድል ቀን ምክንያት በማድረግ ለሁለት ቀናት የሚቆይ የተኩስ አቁም ማወጁን አስታውቋል።
ሚኒስቴሩ ዩክሬንም ይህንኑ የተኩስ አቁም ውሳኔ እንድትከተል ጥሪ ያቀረበ ሲሆን፣ በበዓሉ አከባበር ወቅት በሩሲያ ላይ የሚሰነዘር ማንኛውም ጥቃት ካለ የሚሰጠው የአጸፋ መልስ እጅግ ከባድ እንደሚሆን አስጠንቅቋል።
ይህ መግለጫ የወጣው የዩክሬኑ ፕሬዝዳንት ቮሎዲሚር ዘለንስኪ በሞስኮ ቀይ አደባባይ የሚካሄደውን የድል ቀን ሰልፍ ኪየቭ ኢላማ ልታደርግ እንደምትችል መጠቆማቸውን ተከትሎ መሆኑ ተገልጿል።
የሩሲያ ማስጠንቀቂያም በበዓሉ ላይ ማንኛውንም ዓይነት ችግር ለመፍጠር የሚደረጉ ሙከራዎችን ለመከላከል ያለመ መሆኑ ተመላክቷል።
በቢታኒያ ሲሳይ
#russia #ukraine #victoryday #ceasefire #moscow #zelensky #internationalnews #ethiopia
4 months ago
ኢራን የባሊስቲክ ሚሳይሎቿን አሳየች፤ ፕሬዝዳንት ትራምፕ የተኩስ አቁሙ እንዲቀጥል እንደሚፈልጉ ገለጹ
በኢራን ዋና ከተማ ቴህራን በሺዎች የሚቆጠሩ ኢራናውያን አደባባይ በመውጣት ወታደራዊ ትዕይንት ሲያደርጉ ውለዋል። በዚሁ ወታደራዊ ትዕይንት ላይ የሀገሪቱ ጦር የባሊስቲክ ሚሳይል አርሰናሉንና ዘመናዊ የጦር መሣሪያዎቹን ለዓለም ይፋ አድርጓል።
ይህ ወታደራዊ ጉልበት የማሳየት እርምጃ የመጣው የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በአሁኑ ወቅት ያለውን የተኩስ አቁም ስምምነት (Ceasefire) ላልተወሰነ ጊዜ ለማራዘም እንደሚፈልጉ በገለጹበት ወቅት ነው። ፕሬዝዳንቱ የተኩስ አቁሙ እንዲቀጥል ፍላጎት ቢኖራቸውም፣ በኢራን በኩል እየታየ ያለው ወታደራዊ ዝግጅት በአካባቢው ያለውን የዲፕሎማሲ ውጥረት ዳግም አቀጣጥሎታል።
ኢራን የባሊስቲክ ሚሳይሎቿን በአደባባይ ማሳየቷ ለአሜሪካና ለምዕራባውያን አጋሮቿ "ለማንኛውም ዓይነት ጥቃት ዝግጁ ነን" የሚል መልዕክት እንደሆነ ተንታኞች ይገልጻሉ። በሌላ በኩል ፕሬዝዳንት ትራምፕ የተኩስ አቁሙን ለማራዘም ማቀዳቸው፣ ዋሽንግተን በቀጥታ ጦርነት ውስጥ ከመግባት ይልቅ በዲፕሎማሲያዊና በኢኮኖሚያዊ ጫናዎች ላይ ትኩረት ለማድረግ መፈለጓን እንደሚያሳይ ተመልክቷል።
ይህ ክስተት በቀጣናው ያለው ሠላም ምን ያህል ደካማ እንደሆነና በማንኛውም ጊዜ ወደ ከፋ ግጭት ሊያመራ እንደሚችል ዳግም አረጋግጧል። በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለው የቃላት ጦርነትና ወታደራዊ ፉክክር በቀጣይ ቀናት ወደ ምን ዓይነት አቅጣጫ ሊያመራ እንደሚችል ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ በንቃት እየተከታተለው ይገኛል።
seledadotio
seledadotio
በኢራን ዋና ከተማ ቴህራን በሺዎች የሚቆጠሩ ኢራናውያን አደባባይ በመውጣት ወታደራዊ ትዕይንት ሲያደርጉ ውለዋል። በዚሁ ወታደራዊ ትዕይንት ላይ የሀገሪቱ ጦር የባሊስቲክ ሚሳይል አርሰናሉንና ዘመናዊ የጦር መሣሪያዎቹን ለዓለም ይፋ አድርጓል።
ይህ ወታደራዊ ጉልበት የማሳየት እርምጃ የመጣው የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በአሁኑ ወቅት ያለውን የተኩስ አቁም ስምምነት (Ceasefire) ላልተወሰነ ጊዜ ለማራዘም እንደሚፈልጉ በገለጹበት ወቅት ነው። ፕሬዝዳንቱ የተኩስ አቁሙ እንዲቀጥል ፍላጎት ቢኖራቸውም፣ በኢራን በኩል እየታየ ያለው ወታደራዊ ዝግጅት በአካባቢው ያለውን የዲፕሎማሲ ውጥረት ዳግም አቀጣጥሎታል።
ኢራን የባሊስቲክ ሚሳይሎቿን በአደባባይ ማሳየቷ ለአሜሪካና ለምዕራባውያን አጋሮቿ "ለማንኛውም ዓይነት ጥቃት ዝግጁ ነን" የሚል መልዕክት እንደሆነ ተንታኞች ይገልጻሉ። በሌላ በኩል ፕሬዝዳንት ትራምፕ የተኩስ አቁሙን ለማራዘም ማቀዳቸው፣ ዋሽንግተን በቀጥታ ጦርነት ውስጥ ከመግባት ይልቅ በዲፕሎማሲያዊና በኢኮኖሚያዊ ጫናዎች ላይ ትኩረት ለማድረግ መፈለጓን እንደሚያሳይ ተመልክቷል።
ይህ ክስተት በቀጣናው ያለው ሠላም ምን ያህል ደካማ እንደሆነና በማንኛውም ጊዜ ወደ ከፋ ግጭት ሊያመራ እንደሚችል ዳግም አረጋግጧል። በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለው የቃላት ጦርነትና ወታደራዊ ፉክክር በቀጣይ ቀናት ወደ ምን ዓይነት አቅጣጫ ሊያመራ እንደሚችል ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ በንቃት እየተከታተለው ይገኛል።
seledadotio
seledadotio
4 months ago
''ሊባኖስ ገና ቅጣቷን አልጨረሰችም'' ኔታንያሁ
#ethiopia | በመካከለኛው ምስራቅ ያለው ውጥረት አዲስ መልክ እየያዘ ባለበት በዚህ ወቅት፣ እስራኤል ሌሊቱን ይፋ የተደረገውን ባለ ሁለት ሳምንት የተኩስ አቁም ስምምነት እንደምትደግፍ አስታውቃለች። ይሁን እንጂ ይህ ስምምነት "ሊባኖስን እንደማያካትት" ግልጽ በማድረግ ጉዳዩን ወደ ሌላ አቅጣጫ መልሳዋለች።
የጠቅላይ ሚኒስትር ቤኒያሚን ኔታንያሁ ጽሕፈት ቤት ባወጣው መግለጫ፣ በኢራን እና በምዕራባውያን መካከል የተደረሰውን ስምምነት መቀበሏን አረጋግጧል።
እንደ እስራኤል መግለጫ ከሆነ፣ ለሚቀጥሉት ሁለት ሳምንታት የሚቆየው ይሄው ስምምነት የሚከተሉትን ዋና ዋና ጉዳዮች ይዟል፦
እስራኤል በኢራን ላይ የምታደርሰውን ወታደራዊ እርምጃ ታቆማለች።
ኢራን ወሳኝ የሆነውን የሆርሙዝ የባህር ሰርጥ ለትራንስፖርት ክፍት ታደርጋለች።
ኢራን በአሜሪካ፣ በእስራኤል እና በቀጠናው አገራት ላይ የምታደርሰውን ማንኛውንም ጥቃት ለሁለት ሳምንታት ሙሉ በሙሉ ታቆማለች።
አሜሪካ ኢራን "የኑክሌር፣ የሚሳኤል እና የሽብር ስጋት እንዳትሆን" የምታደርገውን ጥረት እስራኤል እንደምትደግፍ ገልጻለች።
የዚህ ስምምነት ትልቁ አነጋጋሪ ነጥብ በሊባኖስ በኩል ያለው ግንኙነት ነው። የፓኪስታኑ ጠቅላይ ሚኒስትር ሼህባዝ ሻሪፍ ስምምነቱ ሊባኖስንም እንደሚያካትት ቀደም ብለው ቢናገሩም፣ የእስራኤል ወገን ግን ይህንን በፍጹም ውድቅ አድርጎታል።
"ይህ ስምምነት ሊባኖስን አያካትትም" ሲል የኔታንያሁ ቢሮ በግልጽ አስታውቋል።
ይህም ማለት እስራኤል ከኢራን ጋር "ጊዜያዊ ሰላም" ብታወርድም፣ በሰሜን በኩል ከሂዝቦላህ ጋር የምታደርገው ፍልሚያ እንደማይቆም ፍንጭ ሰጥታለች። ቀጠናው ለሁለት ሳምንታት "እፎይ" ቢልም፣ የሊባኖስ ሰማይ ግን አሁንም በስጋት እንደተሸፈነ ነው።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #israel #iran #ceasefire #lebanon #middleeastnews #breakingnews
#ethiopia | በመካከለኛው ምስራቅ ያለው ውጥረት አዲስ መልክ እየያዘ ባለበት በዚህ ወቅት፣ እስራኤል ሌሊቱን ይፋ የተደረገውን ባለ ሁለት ሳምንት የተኩስ አቁም ስምምነት እንደምትደግፍ አስታውቃለች። ይሁን እንጂ ይህ ስምምነት "ሊባኖስን እንደማያካትት" ግልጽ በማድረግ ጉዳዩን ወደ ሌላ አቅጣጫ መልሳዋለች።
የጠቅላይ ሚኒስትር ቤኒያሚን ኔታንያሁ ጽሕፈት ቤት ባወጣው መግለጫ፣ በኢራን እና በምዕራባውያን መካከል የተደረሰውን ስምምነት መቀበሏን አረጋግጧል።
እንደ እስራኤል መግለጫ ከሆነ፣ ለሚቀጥሉት ሁለት ሳምንታት የሚቆየው ይሄው ስምምነት የሚከተሉትን ዋና ዋና ጉዳዮች ይዟል፦
እስራኤል በኢራን ላይ የምታደርሰውን ወታደራዊ እርምጃ ታቆማለች።
ኢራን ወሳኝ የሆነውን የሆርሙዝ የባህር ሰርጥ ለትራንስፖርት ክፍት ታደርጋለች።
ኢራን በአሜሪካ፣ በእስራኤል እና በቀጠናው አገራት ላይ የምታደርሰውን ማንኛውንም ጥቃት ለሁለት ሳምንታት ሙሉ በሙሉ ታቆማለች።
አሜሪካ ኢራን "የኑክሌር፣ የሚሳኤል እና የሽብር ስጋት እንዳትሆን" የምታደርገውን ጥረት እስራኤል እንደምትደግፍ ገልጻለች።
የዚህ ስምምነት ትልቁ አነጋጋሪ ነጥብ በሊባኖስ በኩል ያለው ግንኙነት ነው። የፓኪስታኑ ጠቅላይ ሚኒስትር ሼህባዝ ሻሪፍ ስምምነቱ ሊባኖስንም እንደሚያካትት ቀደም ብለው ቢናገሩም፣ የእስራኤል ወገን ግን ይህንን በፍጹም ውድቅ አድርጎታል።
"ይህ ስምምነት ሊባኖስን አያካትትም" ሲል የኔታንያሁ ቢሮ በግልጽ አስታውቋል።
ይህም ማለት እስራኤል ከኢራን ጋር "ጊዜያዊ ሰላም" ብታወርድም፣ በሰሜን በኩል ከሂዝቦላህ ጋር የምታደርገው ፍልሚያ እንደማይቆም ፍንጭ ሰጥታለች። ቀጠናው ለሁለት ሳምንታት "እፎይ" ቢልም፣ የሊባኖስ ሰማይ ግን አሁንም በስጋት እንደተሸፈነ ነው።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #israel #iran #ceasefire #lebanon #middleeastnews #breakingnews
4 months ago
ዓለም እፎይ ልትል ይሆን?
📌በኢራን እና አሜሪካ መካከል የ45 ቀናት የተኩስ አቁም አንዲደረግ ጥሪ ቀረበ
#ethiopia | በአሜሪካ እና በኢራን መካከል የተፈጠረውን የጦርነት ውጥረት ለማርገብ፣ አሸማጋይ ሀገራት የ45 ቀናት ጊዜያዊ የተኩስ አቁም ጥሪ አቅርበዋል። ፓኪስታን፣ ቱርክ እና ግብፅ ባመቻቹት በዚህ የሽምግልና ጥረት፣ ሁለቱም ተፋላሚ ወገኖች የቀረበላቸውን እቅድ ለመቀበል አዎንታዊ ፍላጎት ማሳየታቸው ተገልጿል።
ይህ የ45 ቀናት የተኩስ አቁም እቅድ፣ በቀጣይ ወደ ዘላቂ ሰላም እና ቋሚ የተኩስ አቁም ሊሸጋገር በሚችልበት መንገድ ላይ ለመምከር የተዘጋጀ ነው። በዚሁ ወሳኝ ውይይት ላይም የኢራኑ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አባስ አራግቺ እንዲሁም የአሜሪካው ልዩ መልዕክተኛ ስቲቭ ዊትኮፍ ተሳትፈዋል።
ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ባለፈው ቅዳሜ ለኢራን ሁለተኛውን የ48 ሰዓታት የጊዜ ገደብ መስጠታቸው የሚታወስ ሲሆን፤ አሁን ላይ አሸማጋዮቹ ያቀረቡት ይህ አዲሱ የስምምነት ሀሳብም በቀጣዮቹ 48 ሰዓታት ውስጥ ወደ ትግበራ ይገባል ተብሎ ይጠበቃል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ኢራን #አሜሪካ #የተኩስ_አቁም #ዓለም_አቀፍ_ዜና #ሰላም #ፖለቲካ #iran #us #ceasefire #geopolitics
📌በኢራን እና አሜሪካ መካከል የ45 ቀናት የተኩስ አቁም አንዲደረግ ጥሪ ቀረበ
#ethiopia | በአሜሪካ እና በኢራን መካከል የተፈጠረውን የጦርነት ውጥረት ለማርገብ፣ አሸማጋይ ሀገራት የ45 ቀናት ጊዜያዊ የተኩስ አቁም ጥሪ አቅርበዋል። ፓኪስታን፣ ቱርክ እና ግብፅ ባመቻቹት በዚህ የሽምግልና ጥረት፣ ሁለቱም ተፋላሚ ወገኖች የቀረበላቸውን እቅድ ለመቀበል አዎንታዊ ፍላጎት ማሳየታቸው ተገልጿል።
ይህ የ45 ቀናት የተኩስ አቁም እቅድ፣ በቀጣይ ወደ ዘላቂ ሰላም እና ቋሚ የተኩስ አቁም ሊሸጋገር በሚችልበት መንገድ ላይ ለመምከር የተዘጋጀ ነው። በዚሁ ወሳኝ ውይይት ላይም የኢራኑ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አባስ አራግቺ እንዲሁም የአሜሪካው ልዩ መልዕክተኛ ስቲቭ ዊትኮፍ ተሳትፈዋል።
ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ባለፈው ቅዳሜ ለኢራን ሁለተኛውን የ48 ሰዓታት የጊዜ ገደብ መስጠታቸው የሚታወስ ሲሆን፤ አሁን ላይ አሸማጋዮቹ ያቀረቡት ይህ አዲሱ የስምምነት ሀሳብም በቀጣዮቹ 48 ሰዓታት ውስጥ ወደ ትግበራ ይገባል ተብሎ ይጠበቃል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ኢራን #አሜሪካ #የተኩስ_አቁም #ዓለም_አቀፍ_ዜና #ሰላም #ፖለቲካ #iran #us #ceasefire #geopolitics
Comments