5 hours ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የስሪላንካ የወንጀል ምርመራ ዲፓርትመንት በካናዳ የተሻለ የስራ ዕድል እንደሚፈጥርላቸው በማታለል ሦስት ዜጎችን በህገወጥ መንገድ ወደ ኢትዮጵያ በማዘዋወር የተጠረጠረን አንድ ስሪላንካዊ በቁጥጥር ስር ማዋሉን አስታወቀ።
ተጎጂዎቹ ዕድሜያቸው ከ25 እስከ 27 የሆኑ የኪሊኖቺ አካባቢ ነዋሪዎች ሲሆኑ፣ የውጭ ሀገር የስራ ዕድል ቃል ተገብቶላቸው በዱባይ አድርገው ወደ ኢትዮጵያ እንዲገቡ ተደርጓል። የወንጀል ምርመራ ዲፓርትመንቱ እንዳስረዳው፣ ተጠርጣሪው ለአውሮፕላን ትኬት እና ለቪዛ በሚል ከተጎጂዎቹ 6.4 ሚሊዮን የስሪላንካ ሩፒ (የገንዘብ መጠን) ተቀብሏል። ይሁን እንጂ ተጎጂዎቹ ኢትዮጵያ ውስጥ ሲደርሱ በተደራጀ ወንጀለኛ ቡድን ታግተው፣ እያንዳንዳቸውን ለመልቀቅ 30 ሺህ የአሜሪካን ዶላር ቤዛ ተጠይቆባቸዋል።
የፖሊስ ሚዲያ ክፍል እንዳብራራው፣ አጋቾቹ ይህንን የቤዛ ገንዘብ ጥያቄ ለተጎጂ ቤተሰቦች ያደረሱት ጉዞውን ባመቻቸው በዚሁ ግለሰብ በኩል ሲሆን፣ ቤተሰቦቹም ከ20 ሚሊዮን ሩፒ በላይ ከፍለዋል ተብሏል። ሜይ 27 ቀን 2026 በመከላከያ ሚኒስቴር በኩል የቀረበውን አቤቱታ ተከትሎ፣ የህገወጥ የሰዎች ዝውውር እና የባህር ላይ ወንጀል ምርመራ ክፍል ሰፊ ማጣራት ጀምሮ ነበር። ለዚህ ምርመራ በኢትዮጵያ የሚገኘው የስሪላንካ ኤምባሲ እና የኢትዮጵያ የፀጥታ አካላት ከፍተኛ ትብብር ማድረጋቸው ተገልጿል።
የተደረገውን ክትትል ተከትሎ የኢትዮጵያ የፀጥታ አካላት ሦስቱን ስሪላንካውያን በሰላም ከማስለቀቃቸውም በላይ፣ ከዚህ የተደራጀ ወንጀል ጋር ግንኙነት አላቸው የተባሉ አራት ፓኪስታናውያን እና አንድ ኢትዮጵያዊን በቁጥጥር ስር አውለዋል። በስሪላንካ በኩልም የተጎጂዎቹን ጉዞ ሲያመቻች የነበረው እና የኪሊኖቺ ነዋሪ የሆነው ተጠርጣሪ በቁጥጥር ስር ውሏል።
በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ የሚገኘው የስሪላንካ ኤምባሲ ኃላፊዎች አስፈላጊውን ማጣራት ካደረጉ በኋላ፣ ተጎጂዎቹ ወደ ሀገራቸው እንዲመለሱ እየተደረገ ይገኛል። የስሪላንካ የወንጀል ምርመራ ዲፓርትመንትም በቁጥጥር ስር በዋለው ግለሰብ እና በወንጀለኞች መረቡ መካከል ያለውን ሰፋ ያለ ትስስር ለማጋለጥ ምርመራውን አጠናክሮ ቀጥሏል።
ተጎጂዎቹ ዕድሜያቸው ከ25 እስከ 27 የሆኑ የኪሊኖቺ አካባቢ ነዋሪዎች ሲሆኑ፣ የውጭ ሀገር የስራ ዕድል ቃል ተገብቶላቸው በዱባይ አድርገው ወደ ኢትዮጵያ እንዲገቡ ተደርጓል። የወንጀል ምርመራ ዲፓርትመንቱ እንዳስረዳው፣ ተጠርጣሪው ለአውሮፕላን ትኬት እና ለቪዛ በሚል ከተጎጂዎቹ 6.4 ሚሊዮን የስሪላንካ ሩፒ (የገንዘብ መጠን) ተቀብሏል። ይሁን እንጂ ተጎጂዎቹ ኢትዮጵያ ውስጥ ሲደርሱ በተደራጀ ወንጀለኛ ቡድን ታግተው፣ እያንዳንዳቸውን ለመልቀቅ 30 ሺህ የአሜሪካን ዶላር ቤዛ ተጠይቆባቸዋል።
የፖሊስ ሚዲያ ክፍል እንዳብራራው፣ አጋቾቹ ይህንን የቤዛ ገንዘብ ጥያቄ ለተጎጂ ቤተሰቦች ያደረሱት ጉዞውን ባመቻቸው በዚሁ ግለሰብ በኩል ሲሆን፣ ቤተሰቦቹም ከ20 ሚሊዮን ሩፒ በላይ ከፍለዋል ተብሏል። ሜይ 27 ቀን 2026 በመከላከያ ሚኒስቴር በኩል የቀረበውን አቤቱታ ተከትሎ፣ የህገወጥ የሰዎች ዝውውር እና የባህር ላይ ወንጀል ምርመራ ክፍል ሰፊ ማጣራት ጀምሮ ነበር። ለዚህ ምርመራ በኢትዮጵያ የሚገኘው የስሪላንካ ኤምባሲ እና የኢትዮጵያ የፀጥታ አካላት ከፍተኛ ትብብር ማድረጋቸው ተገልጿል።
የተደረገውን ክትትል ተከትሎ የኢትዮጵያ የፀጥታ አካላት ሦስቱን ስሪላንካውያን በሰላም ከማስለቀቃቸውም በላይ፣ ከዚህ የተደራጀ ወንጀል ጋር ግንኙነት አላቸው የተባሉ አራት ፓኪስታናውያን እና አንድ ኢትዮጵያዊን በቁጥጥር ስር አውለዋል። በስሪላንካ በኩልም የተጎጂዎቹን ጉዞ ሲያመቻች የነበረው እና የኪሊኖቺ ነዋሪ የሆነው ተጠርጣሪ በቁጥጥር ስር ውሏል።
በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ የሚገኘው የስሪላንካ ኤምባሲ ኃላፊዎች አስፈላጊውን ማጣራት ካደረጉ በኋላ፣ ተጎጂዎቹ ወደ ሀገራቸው እንዲመለሱ እየተደረገ ይገኛል። የስሪላንካ የወንጀል ምርመራ ዲፓርትመንትም በቁጥጥር ስር በዋለው ግለሰብ እና በወንጀለኞች መረቡ መካከል ያለውን ሰፋ ያለ ትስስር ለማጋለጥ ምርመራውን አጠናክሮ ቀጥሏል።
8 hours ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የኢስቶኒያ ፖሊስ ኦገስት ሦስት ቀን በዋና ከተማዋ ታሊን ውስጥ፣ ሀገሪቱን በህገወጥ መንገድ አቋርጠው ገብተዋል በሚል ጥርጣሬ በሁለት ቡድን የተከፈሉ ስምንት ሰዎችን በቁጥጥር ስር አውሏል። የሰሜናዊ ፖሊስ እዝ የፕሬስ አገልግሎት እንዳስታወቀው፣ በመጀመሪያ በታሊን በሚገኘው ታምሳሬ ፓርክ ውስጥ ስድስት ሰዎች የተያዙ ሲሆን፣ ግለሰቦቹ ከኢትዮጵያ እንደመጡ እና ወደ አውሮፓ የገቡትም ቤላሩስን አቋርጠው መሆኑን ለፖሊስ ተናግረዋል።
በዚሁ ዕለት በከተማዋ መሀል ተጨማሪ ሁለት ግለሰቦች የተያዙ ሲሆን፣ እነዚህም በተመሳሳይ ከኢትዮጵያ እንደመጡ ተናግረዋል። ሁለቱ ግለሰቦች ምንም ዓይነት የማንነት መታወቂያ ሰነድ ያልነበራቸው ሲሆን፣ ከዚህ ቀደም ከተያዙት ስድስት ሰዎች ጋር በመሆን ሁሉም ለውጭ ዜጎች ወደተዘጋጀው ጊዜያዊ ማቆያ ማዕከል ተወስደዋል።
በኢስቶኒያ ባለፉት ጥቂት ሳምንታት ውስጥ በደርዘን የሚቆጠሩ ህገወጥ ስደተኞች በቁጥጥር ስር መዋላቸው ተዘግቧል። የሀገሪቱ ፖሊስ እንዳረጋገጠው፣ የተደራጁ ወንጀለኛ ቡድኖች ስደተኞቹን በኢስቶኒያ አቋርጠው ወደ ሌሎች ሀገራት ለማሻገር ሙከራ እያደረጉ ይገኛሉ።
በዚሁ ዕለት በከተማዋ መሀል ተጨማሪ ሁለት ግለሰቦች የተያዙ ሲሆን፣ እነዚህም በተመሳሳይ ከኢትዮጵያ እንደመጡ ተናግረዋል። ሁለቱ ግለሰቦች ምንም ዓይነት የማንነት መታወቂያ ሰነድ ያልነበራቸው ሲሆን፣ ከዚህ ቀደም ከተያዙት ስድስት ሰዎች ጋር በመሆን ሁሉም ለውጭ ዜጎች ወደተዘጋጀው ጊዜያዊ ማቆያ ማዕከል ተወስደዋል።
በኢስቶኒያ ባለፉት ጥቂት ሳምንታት ውስጥ በደርዘን የሚቆጠሩ ህገወጥ ስደተኞች በቁጥጥር ስር መዋላቸው ተዘግቧል። የሀገሪቱ ፖሊስ እንዳረጋገጠው፣ የተደራጁ ወንጀለኛ ቡድኖች ስደተኞቹን በኢስቶኒያ አቋርጠው ወደ ሌሎች ሀገራት ለማሻገር ሙከራ እያደረጉ ይገኛሉ።
11 hours ago
ከሁለት ሚሊየን ብር በላይ የሚገመት የወንዶች አልባሳትን የሰረቁ 6 ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ዋሉ
የወንጀል ድርጊቱ የተፈፀመው ሐምሌ 21 ቀን 2018 ዓ/ም ከሌሊቱ 9 ሠዓት በልደታ ክ/ከተማ ወረዳ 1 መቻሬ ሜዳ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ነው።
ተጠርጣሪዎቹ ደብሩ መለሰ፣ ሞገስ ተካይ፣ ብርሃኑ አያሌው፣ ዘሪሁን በለጠ፣ ሚሊዮን መስፍን እና አብዱልሰላም ነስረዲን የተባሉ ሲሆኑ የሠሌዳ ቁጥር ኮድ 3 B 40762 አዲስ አበባ የሆነ ቪትስ ተሽከርካሪ በመጠቀም አንድ የወንዶች አልባሳት መሸጫ ሱቅ ገንጥለው ገብተዋል።
ግምታዊ ዋጋቸው ከሁለት ሚሊዮን ብር በላይ የሚያወጡ የወንዶች ሱሪ፣ ጫማ እና ቲሸርቶችን ሰርቀው ሊሰወሩ ሲሉ ድርጊቱን በተመለከቱ ግለሰቦች እና በፖሊስ አባላት በቁጥጥር ስር ውለዋል፡፡
ፖሊስ በወቅቱ ተጠርጣሪዎቹን በቁጥጥር ስር ባዋለበት ወቅት ባደረገው ፍተሻ ከሌሎች ክፍለ ከተሞች ከሰረቁት የጎማ ጎሚኒ እና የኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ ኬብል ጋር በቁጥጥር ስር ውለው ምርመራ እየተጣራባቸው እንደሚገኝ የልደታ ክ/ከተማ ፖሊስ ዋና መምሪያ ገልጾ ተገቢውን ማስረጃ በማጠናቀር ክስ እንደሚያስመሰርትም አስታውቋል፡፡
የክረምት ወቅት እንደመሆኑ መጠን ጨለማን እና ዝናብን እንደምቹ አጋጣሚ በመጠቀም የሚፈፀሙ ወንጀሎችን ለመከላከል የንግድ ተቋማትም ሆኑ ድርጅቶች የጥበቃ አቅማቸውን ማጠናከር እንደሚጠበቅባቸውም የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ አስታውቋል፡፡
Seledadotio
Seledadotio
የወንጀል ድርጊቱ የተፈፀመው ሐምሌ 21 ቀን 2018 ዓ/ም ከሌሊቱ 9 ሠዓት በልደታ ክ/ከተማ ወረዳ 1 መቻሬ ሜዳ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ነው።
ተጠርጣሪዎቹ ደብሩ መለሰ፣ ሞገስ ተካይ፣ ብርሃኑ አያሌው፣ ዘሪሁን በለጠ፣ ሚሊዮን መስፍን እና አብዱልሰላም ነስረዲን የተባሉ ሲሆኑ የሠሌዳ ቁጥር ኮድ 3 B 40762 አዲስ አበባ የሆነ ቪትስ ተሽከርካሪ በመጠቀም አንድ የወንዶች አልባሳት መሸጫ ሱቅ ገንጥለው ገብተዋል።
ግምታዊ ዋጋቸው ከሁለት ሚሊዮን ብር በላይ የሚያወጡ የወንዶች ሱሪ፣ ጫማ እና ቲሸርቶችን ሰርቀው ሊሰወሩ ሲሉ ድርጊቱን በተመለከቱ ግለሰቦች እና በፖሊስ አባላት በቁጥጥር ስር ውለዋል፡፡
ፖሊስ በወቅቱ ተጠርጣሪዎቹን በቁጥጥር ስር ባዋለበት ወቅት ባደረገው ፍተሻ ከሌሎች ክፍለ ከተሞች ከሰረቁት የጎማ ጎሚኒ እና የኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ ኬብል ጋር በቁጥጥር ስር ውለው ምርመራ እየተጣራባቸው እንደሚገኝ የልደታ ክ/ከተማ ፖሊስ ዋና መምሪያ ገልጾ ተገቢውን ማስረጃ በማጠናቀር ክስ እንደሚያስመሰርትም አስታውቋል፡፡
የክረምት ወቅት እንደመሆኑ መጠን ጨለማን እና ዝናብን እንደምቹ አጋጣሚ በመጠቀም የሚፈፀሙ ወንጀሎችን ለመከላከል የንግድ ተቋማትም ሆኑ ድርጅቶች የጥበቃ አቅማቸውን ማጠናከር እንደሚጠበቅባቸውም የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ አስታውቋል፡፡
Seledadotio
Seledadotio
19 hours ago
ፖለቲከኛ አቶ አበባ አካሉ መታሰራቸው ተሰማ
በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ሰፋ ያለ ትንታኔ በመስጠት እና በፓርቲ ፖለቲካ የሚታወቁት አቶ አበበ በትናንትናው ዕለት መታሰራቸውን የቤተሰብ ምንጮች ለአንዳፍታ ሚዲያ ተናግረዋል፡፡
ፖለቲከኛው በምን ምክንያት እንደታሰሩ ያልታወቀ ሲሆን፤ ባሁኑ ሰአት ሜክሲኮ በሚገኘው የፌዴራል ፖሊስ እንደሚገኙም ቤተሰቦቻቸው ገልጸዋል፡፡
Seledadotio
Seledadotio
በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ሰፋ ያለ ትንታኔ በመስጠት እና በፓርቲ ፖለቲካ የሚታወቁት አቶ አበበ በትናንትናው ዕለት መታሰራቸውን የቤተሰብ ምንጮች ለአንዳፍታ ሚዲያ ተናግረዋል፡፡
ፖለቲከኛው በምን ምክንያት እንደታሰሩ ያልታወቀ ሲሆን፤ ባሁኑ ሰአት ሜክሲኮ በሚገኘው የፌዴራል ፖሊስ እንደሚገኙም ቤተሰቦቻቸው ገልጸዋል፡፡
Seledadotio
Seledadotio
1 day ago
ደህንነት ነኝ በማለት የማጭበርበር ወንጀል ሲፈፅም የነበረው ግለሰብ በእስራት እና በገንዘብ ተቀጣ
በአምቦ ከተማ ውስጥ ደህንነት ነኝ በማለት የማጭበርበር ወንጀል ሲፈፅም የነበረው ግለሰብ በእስራት እና በገንዘብ መቀጣቱ ተገልጿል ።የአምቦ ከተማ ፖሊስ ዋና መምሪያ የኮሚኒኬሽን ፅ/ቤት ሃላፊ ረዳት ኢንስፔክተር አቡሽ ማሞ ለብስራት ሬዲዮ እንደገለፁት ተከሳሽ ዘሪሁን ጉርሙ የሰላሳ ዓመት ግለሰብ ነው።
በከተማዋ ውስጥ በመዘዋወር " እኔ ደህንነት ነኝ " በወንጀል የተጠረጠሩ ሰዎችን አስፈታለሁ በማለት የማጭበርበር ወንጀል ፈፅሟል።ተከሳሹ አንዲት የአምቦ ከተማ ነዋሪ የሆነች ግለሰብን ባለቤትሽን ከተጠረጠረበት የወንጀል ድርጊት ነፃ እንዲወጣ አደርጋለሁ በማለት ከግለሰቧ ላይ 120 ሺህ ብር ሲቀበል በቁጥጥር ስር ውሏል ።
ፖሊስም በተከሳሹ ላይ አስፈላጊውን የምርመራ መዝገብ በተገቢው ማስረጃ በማጠናከር ለአቃቤህግ ልኳል። አቃቤ ህግም ከፖሊስ የተላከውን የምርመራ መዝገብ ተመልክቶ በአታላይነት ወንጀል ክስ መስርቶበታል።ክሱን የተመለከተው የአምቦ ከተማ ወረዳ ፍርድ ቤት ሃምሌ 17 ቀን 2018 ዓ.ም በዋለው ችሎት ተከሳሽ ዘሪሁን ጉርሙ የራሱን ማንነትና ሁኔታ በመሰወር፣ አሳሳች ነገሮችን በመናገር እና ደህንነት ነኝ በማለት በፈፀመው የማጭበርበር ወንጀል ጥፋተኛ መሆኑ ተረጋግጧል ።
በዚህም መሰረት በሁለት ዓመት ከ9ወር እስራትና በአንድ ሺህ ብር የገንዘብ መቀጮ ፣ እንዲቀጣ የተወሰነበት መሆኑን ረዳት ኢንስፔክተር አቡሽ ማሞ ጨምረው ለብስራት ሬዲዮ ገልፀዋል።
Seledadotio
Seledadotio
በአምቦ ከተማ ውስጥ ደህንነት ነኝ በማለት የማጭበርበር ወንጀል ሲፈፅም የነበረው ግለሰብ በእስራት እና በገንዘብ መቀጣቱ ተገልጿል ።የአምቦ ከተማ ፖሊስ ዋና መምሪያ የኮሚኒኬሽን ፅ/ቤት ሃላፊ ረዳት ኢንስፔክተር አቡሽ ማሞ ለብስራት ሬዲዮ እንደገለፁት ተከሳሽ ዘሪሁን ጉርሙ የሰላሳ ዓመት ግለሰብ ነው።
በከተማዋ ውስጥ በመዘዋወር " እኔ ደህንነት ነኝ " በወንጀል የተጠረጠሩ ሰዎችን አስፈታለሁ በማለት የማጭበርበር ወንጀል ፈፅሟል።ተከሳሹ አንዲት የአምቦ ከተማ ነዋሪ የሆነች ግለሰብን ባለቤትሽን ከተጠረጠረበት የወንጀል ድርጊት ነፃ እንዲወጣ አደርጋለሁ በማለት ከግለሰቧ ላይ 120 ሺህ ብር ሲቀበል በቁጥጥር ስር ውሏል ።
ፖሊስም በተከሳሹ ላይ አስፈላጊውን የምርመራ መዝገብ በተገቢው ማስረጃ በማጠናከር ለአቃቤህግ ልኳል። አቃቤ ህግም ከፖሊስ የተላከውን የምርመራ መዝገብ ተመልክቶ በአታላይነት ወንጀል ክስ መስርቶበታል።ክሱን የተመለከተው የአምቦ ከተማ ወረዳ ፍርድ ቤት ሃምሌ 17 ቀን 2018 ዓ.ም በዋለው ችሎት ተከሳሽ ዘሪሁን ጉርሙ የራሱን ማንነትና ሁኔታ በመሰወር፣ አሳሳች ነገሮችን በመናገር እና ደህንነት ነኝ በማለት በፈፀመው የማጭበርበር ወንጀል ጥፋተኛ መሆኑ ተረጋግጧል ።
በዚህም መሰረት በሁለት ዓመት ከ9ወር እስራትና በአንድ ሺህ ብር የገንዘብ መቀጮ ፣ እንዲቀጣ የተወሰነበት መሆኑን ረዳት ኢንስፔክተር አቡሽ ማሞ ጨምረው ለብስራት ሬዲዮ ገልፀዋል።
Seledadotio
Seledadotio
Sponsored by
Surafel
1 day ago
በፖሊስ የአደን ማስታወቂያ የወጣበት ተጠርጣሪ የተሻለ የሰልፊ ፎቶውን ለፖሊስ ላከ
#ethiopia | ከአስር ዓመት በፊት እንዲህ ሆነ።በአሜሪካ ኦሃዮ ግዛት የሚገኘው የሊማ ፖሊስ መምሪያ በፍርድ ቤት ያልቀረበውን ዶናልድ “ቺፕ” ፑግ የተባለ ተፈላጊ ግለሰብ ለማደን በፌስቡክ ገጹ የፍለጋ ማስታወቂያ አወጣ።
ነገር ግን ተፈላጊው ግለሰብ ከመሸሸግ ይልቅ በፖሊስ የወጣው የመታወቂያ ፎቶው እንደማያምርበት በመግለጽ “ይህ የተሻለ ፎቶ ነው፤ ያኛው አስቀያሚ ነው” የሚል አጭር መልእክት ከተሻለ የሰልፊ ፎቶው ጋር ለፖሊስ ልኳል።
የሊማ ፖሊስም መልእክቱን አይቶ እንዳላየ ከማለፍ ይልቅ ግለሰቡ ላደረገው “ትብብር” በፌስቡክ ገጹ ላይ አመስግኖ አዲሱን የሰልፊ ፎቶ የለጠፈው ሲሆን፣ እጁንም እንዲሰጥ አሳሰበ።
በሁለቱ አካላት መካከል የተደረገው ይህ ድንቅ ውይይት በማህበራዊ ሚዲያ ተሰራጭቶ ሰዎች የተጋሩት ሲሆን፣ የብዙዎችን አስገርሟል።
ዶናልድ ፑግ ከጥቂት ቀናት በኋላ በፍሎሪዳ ግዛት በቁጥጥር ስር የዋለ ቢሆንም የላከው ሰልፊ በቅርብ ዓመታት ከተመዘገቡት እጅግ አስገራሚ የፖሊስ የፍለጋ ማስታወቂያዎች አንዱ ሆኖ ተመዝግቧል።
በያፌት ገ/ህይወት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#ethiopia | ከአስር ዓመት በፊት እንዲህ ሆነ።በአሜሪካ ኦሃዮ ግዛት የሚገኘው የሊማ ፖሊስ መምሪያ በፍርድ ቤት ያልቀረበውን ዶናልድ “ቺፕ” ፑግ የተባለ ተፈላጊ ግለሰብ ለማደን በፌስቡክ ገጹ የፍለጋ ማስታወቂያ አወጣ።
ነገር ግን ተፈላጊው ግለሰብ ከመሸሸግ ይልቅ በፖሊስ የወጣው የመታወቂያ ፎቶው እንደማያምርበት በመግለጽ “ይህ የተሻለ ፎቶ ነው፤ ያኛው አስቀያሚ ነው” የሚል አጭር መልእክት ከተሻለ የሰልፊ ፎቶው ጋር ለፖሊስ ልኳል።
የሊማ ፖሊስም መልእክቱን አይቶ እንዳላየ ከማለፍ ይልቅ ግለሰቡ ላደረገው “ትብብር” በፌስቡክ ገጹ ላይ አመስግኖ አዲሱን የሰልፊ ፎቶ የለጠፈው ሲሆን፣ እጁንም እንዲሰጥ አሳሰበ።
በሁለቱ አካላት መካከል የተደረገው ይህ ድንቅ ውይይት በማህበራዊ ሚዲያ ተሰራጭቶ ሰዎች የተጋሩት ሲሆን፣ የብዙዎችን አስገርሟል።
ዶናልድ ፑግ ከጥቂት ቀናት በኋላ በፍሎሪዳ ግዛት በቁጥጥር ስር የዋለ ቢሆንም የላከው ሰልፊ በቅርብ ዓመታት ከተመዘገቡት እጅግ አስገራሚ የፖሊስ የፍለጋ ማስታወቂያዎች አንዱ ሆኖ ተመዝግቧል።
በያፌት ገ/ህይወት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
1 day ago
ለጥገና ሥራ የሚቋረጥ የኃይል አቅርቦት
ነገ ሐምሌ 28 ቀን 2018 ዓ.ም የጥገና ሥራ ለማከናዎን የኃይል አቅርቦት የሚቋረጥባቸው አካባቢዎች፦
✅ ከጠዋቱ 2፡00-11፡00
👉ጎጃም በረንዳ ጫፍ፣ ጳውሎስ ሆስፒታል፣ ሀግቤስ አራት መንታ፣ ጅንአድ፣ አበበች ጎበና፣ ፓስተር አደባባይ፣ አቤት ሆስፒታል፣ ቅዱስ ዮሐንስ ቤ/ክ፣ ሰን ሆቴል፣ 3ኛ ፖሊስ ጣቢ፣ አዲስ አበባ ሜዲካል ኮሌጅ እና አካባቢው፣
👉 ዳውን ታውን ሆቴል፣ አውራሪስ ሆቴል፣ አዲሱ ስታዲየም፣ ካልዲስ ቡና፣ መድሓኒዓለም ቤ/ክ እና አካባቢው፣
✅ ከጠዋቱ 3፡00 - 10፡00
👉 ጉርድ ሾላ፣ ትምህርት መሳሪያዎች ማምረቻ ድርጅት፣ ግብርና ምርምር፣ ጃክሮስ አደባባይ በስተጀርባ እና አካባቢው፣
👉 ላምበረት መናኸሪያ ፣ ላመበረት፣ እስራኤል ኤምባሲ፣ አቢሲኒያ ሆቴል፣ ሱሉልታ እና አካባቢው፣
✅ ከጠዋቱ 4፡00 - 8፡00
👉 ከደንበሯ ሆስፒታል ፣ በግ ተራ፣ ምስራቅ አጠቃላይ፣ ሾላ ገበያ፣ የካ መንፈሻ፣ ዘፍመሽ ሞል፣ እና አካባቢው፣
👉 አትላስ ሆቴል፣ ሻላ መናፈሻ፣ ኤስኦኤስ፣ ደሳለኝ ሆተል ጀርባ፣ ደሳለኝ ሆቴል፣ ፕሬዚደንሺያል ሆቴል፣ሩዋንዳ ኦቨርፓስ እና አካባቢው፣
✅ ከጠዋቱ 3፡00 - 11፡00
👉በጭሮ ሪጅን ደደር፣ ሜታ ፣ መልካ በሎ ፣ ጎሮ ጉቱ ወረዳዎች እና አካባቢው፣
✅ ከጠዋቱ 3፡00 - 11፡00
በበህርዳር ሪጅን ቀበሌ 16 ነጋድራስ በቄ ሰፈር፣ ዶንጎስ መኪና ማሰልጠኛ፣ቤዛ ብዙሃን ት/ቤት እና አካባቢው የኃይል አቅርቦት ተቋርጦ ይቆያል፡፡
ስለሆነም በተጠቀሱት አካባቢዎች የምትገኙ ክቡራን ደንበኞቻችን የጥገና ሥራው ተጠናቆ የኃይል አቅርቦቱ እስኪ መለስ ድረስ በትዕግስት እንድትጠብቁን በትህትና እንጠይቃለን።
#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት
Seledadotio
Seledadotio
ነገ ሐምሌ 28 ቀን 2018 ዓ.ም የጥገና ሥራ ለማከናዎን የኃይል አቅርቦት የሚቋረጥባቸው አካባቢዎች፦
✅ ከጠዋቱ 2፡00-11፡00
👉ጎጃም በረንዳ ጫፍ፣ ጳውሎስ ሆስፒታል፣ ሀግቤስ አራት መንታ፣ ጅንአድ፣ አበበች ጎበና፣ ፓስተር አደባባይ፣ አቤት ሆስፒታል፣ ቅዱስ ዮሐንስ ቤ/ክ፣ ሰን ሆቴል፣ 3ኛ ፖሊስ ጣቢ፣ አዲስ አበባ ሜዲካል ኮሌጅ እና አካባቢው፣
👉 ዳውን ታውን ሆቴል፣ አውራሪስ ሆቴል፣ አዲሱ ስታዲየም፣ ካልዲስ ቡና፣ መድሓኒዓለም ቤ/ክ እና አካባቢው፣
✅ ከጠዋቱ 3፡00 - 10፡00
👉 ጉርድ ሾላ፣ ትምህርት መሳሪያዎች ማምረቻ ድርጅት፣ ግብርና ምርምር፣ ጃክሮስ አደባባይ በስተጀርባ እና አካባቢው፣
👉 ላምበረት መናኸሪያ ፣ ላመበረት፣ እስራኤል ኤምባሲ፣ አቢሲኒያ ሆቴል፣ ሱሉልታ እና አካባቢው፣
✅ ከጠዋቱ 4፡00 - 8፡00
👉 ከደንበሯ ሆስፒታል ፣ በግ ተራ፣ ምስራቅ አጠቃላይ፣ ሾላ ገበያ፣ የካ መንፈሻ፣ ዘፍመሽ ሞል፣ እና አካባቢው፣
👉 አትላስ ሆቴል፣ ሻላ መናፈሻ፣ ኤስኦኤስ፣ ደሳለኝ ሆተል ጀርባ፣ ደሳለኝ ሆቴል፣ ፕሬዚደንሺያል ሆቴል፣ሩዋንዳ ኦቨርፓስ እና አካባቢው፣
✅ ከጠዋቱ 3፡00 - 11፡00
👉በጭሮ ሪጅን ደደር፣ ሜታ ፣ መልካ በሎ ፣ ጎሮ ጉቱ ወረዳዎች እና አካባቢው፣
✅ ከጠዋቱ 3፡00 - 11፡00
በበህርዳር ሪጅን ቀበሌ 16 ነጋድራስ በቄ ሰፈር፣ ዶንጎስ መኪና ማሰልጠኛ፣ቤዛ ብዙሃን ት/ቤት እና አካባቢው የኃይል አቅርቦት ተቋርጦ ይቆያል፡፡
ስለሆነም በተጠቀሱት አካባቢዎች የምትገኙ ክቡራን ደንበኞቻችን የጥገና ሥራው ተጠናቆ የኃይል አቅርቦቱ እስኪ መለስ ድረስ በትዕግስት እንድትጠብቁን በትህትና እንጠይቃለን።
#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት
Seledadotio
Seledadotio
2 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) ባለፈው ሳምንት በሌክ ታሆ ውስጥ ሰጥሞ ህይወቱ ያለፈው ኢትዮጵያዊው የአማዞን ሶፍትዌር መሃንዲስ ጓደኞች፣ በህይወቱ የመጨረሻ ደቂቃዎች ውስጥ በትክክል ምን እንደተፈጠረ ለማወቅ የአይን እማኞች መረጃ በመስጠት እንዲተባበሯቸው ጥሪ አቀረቡ።
የ32 ዓመቱ የኦስቲን ቴክሳስ ነዋሪ የሆነው ትውልደ ኢትዮጵያዊው ያደሳ እምሩ አጋ፣ ጁላይ 27 ቀን በኔቫዳ የባህር ዳርቻ በሚገኘው ሳንድ ሀርበር አቅራቢያ ውሃ ውስጥ እያለ ራሱን ስቶ ነበር። በአካባቢው የነበሩ ሰዎች ወደ ዳርቻው ያወጡት ሲሆን፣ ፖሊሶች እና የህክምና ባለሙያዎች ህይወቱን ለመታደግ ያደረጉት ጥረት ሳይሳካ ቀርቷል።
የዋሾ ካውንቲ ፖሊስ ሞቱን እንደ ድንገተኛ የውሃ ውስጥ የመስመጥ አደጋ እየመረመረው ይገኛል። ሆኖም የካውንቲው የህክምና መርማሪ የመጨረሻውን የሞት ምክንያት እስካሁን ይፋ ስላላደረገ፣ የያደሳ ጓደኞች እና ዘመዶች በውሃው ውስጥ በትክክል ምን እንደተፈጠረ ግልጽ የሆነ መረጃ ለማግኘት እየጣሩ ነው።
በሬዲት ላይ ራሱን የሟች የቅርብ ጓደኛ መሆኑን የገለጸ ግለሰብ፣ በዚያ ምሽት ሳንድ ሀርበር የነበረ ማንኛውም ሰው ፎቶግራፎችን፣ ቪዲዮዎችን ወይም በአካል የተመለከተውን መረጃ እንዲያካፍል ጠይቋል።
እንደ ጸሃፊው ገለጻ ያደሳ ጀምበር ልትጠልቅ ስትል ከሌሎች ጋር እየዋኘ እንደነበር እና ከዚያም ከውሃው ውስጥ የድረሱልኝ ጩኸት እንደተሰማ የአይን እማኞች ተናግረዋል። ሁለት ጓደኞቹ እሱን ለማዳን ሲሞክሩ እንደተቸገሩ እና በፓድል ቦርድ ላይ የነበሩ ሰዎች ሶስቱንም ዋናተኞች ወደ ዳርቻው ለማውጣት እንደረዱ ተገልጿል።
በሌላ በኩል ደግሞ የያደሳ የሊንክድኢን ፕሮፋይል ፎቶግራፍ ታችኛው ግራ ጥግ ላይ በትንሽ ፊደላት "አዝናለሁ !!!!!" (I am Sorry !!!!!) የሚል ጽሑፍ መገኘቱ ብዙዎችን አነጋግሯል። ይህ ጽሑፍ የሚታየው ምስሉ ሲጎላ ብቻ መሆኑ ጉዳዩን ይበልጥ እንቆቅልሽ አድርጎታል።
ለሟች መታሰቢያ የተከፈተው የገንዘብ ማሰባሰቢያ ገጽ (GoFundMe) እንዳስነበበው፣ ያደሳ ከቤተክርስቲያን ኮንፈረንስ እየተመለሰ በሌክ ታሆ ከጓደኞቹ ጋር ጊዜ እያሳለፈ በነበረበት ወቅት አደጋው ያጋጠመው እጅግ መንፈሳዊ ወጣት ነበር። በደግነቱ፣ በሞቅታው እና በለጋስነቱ የሚታወቅ መሆኑን የገለጸው ማሰባሰቢያው፣ የሚሰበሰበው ገንዘብ ለቀብር ስነ-ስርዓት እና አስከሬኑን ወደ ሀገሩ ኢትዮጵያ ለመመለስ እንደሚውል አስታውቋል።
የ32 ዓመቱ የኦስቲን ቴክሳስ ነዋሪ የሆነው ትውልደ ኢትዮጵያዊው ያደሳ እምሩ አጋ፣ ጁላይ 27 ቀን በኔቫዳ የባህር ዳርቻ በሚገኘው ሳንድ ሀርበር አቅራቢያ ውሃ ውስጥ እያለ ራሱን ስቶ ነበር። በአካባቢው የነበሩ ሰዎች ወደ ዳርቻው ያወጡት ሲሆን፣ ፖሊሶች እና የህክምና ባለሙያዎች ህይወቱን ለመታደግ ያደረጉት ጥረት ሳይሳካ ቀርቷል።
የዋሾ ካውንቲ ፖሊስ ሞቱን እንደ ድንገተኛ የውሃ ውስጥ የመስመጥ አደጋ እየመረመረው ይገኛል። ሆኖም የካውንቲው የህክምና መርማሪ የመጨረሻውን የሞት ምክንያት እስካሁን ይፋ ስላላደረገ፣ የያደሳ ጓደኞች እና ዘመዶች በውሃው ውስጥ በትክክል ምን እንደተፈጠረ ግልጽ የሆነ መረጃ ለማግኘት እየጣሩ ነው።
በሬዲት ላይ ራሱን የሟች የቅርብ ጓደኛ መሆኑን የገለጸ ግለሰብ፣ በዚያ ምሽት ሳንድ ሀርበር የነበረ ማንኛውም ሰው ፎቶግራፎችን፣ ቪዲዮዎችን ወይም በአካል የተመለከተውን መረጃ እንዲያካፍል ጠይቋል።
እንደ ጸሃፊው ገለጻ ያደሳ ጀምበር ልትጠልቅ ስትል ከሌሎች ጋር እየዋኘ እንደነበር እና ከዚያም ከውሃው ውስጥ የድረሱልኝ ጩኸት እንደተሰማ የአይን እማኞች ተናግረዋል። ሁለት ጓደኞቹ እሱን ለማዳን ሲሞክሩ እንደተቸገሩ እና በፓድል ቦርድ ላይ የነበሩ ሰዎች ሶስቱንም ዋናተኞች ወደ ዳርቻው ለማውጣት እንደረዱ ተገልጿል።
በሌላ በኩል ደግሞ የያደሳ የሊንክድኢን ፕሮፋይል ፎቶግራፍ ታችኛው ግራ ጥግ ላይ በትንሽ ፊደላት "አዝናለሁ !!!!!" (I am Sorry !!!!!) የሚል ጽሑፍ መገኘቱ ብዙዎችን አነጋግሯል። ይህ ጽሑፍ የሚታየው ምስሉ ሲጎላ ብቻ መሆኑ ጉዳዩን ይበልጥ እንቆቅልሽ አድርጎታል።
ለሟች መታሰቢያ የተከፈተው የገንዘብ ማሰባሰቢያ ገጽ (GoFundMe) እንዳስነበበው፣ ያደሳ ከቤተክርስቲያን ኮንፈረንስ እየተመለሰ በሌክ ታሆ ከጓደኞቹ ጋር ጊዜ እያሳለፈ በነበረበት ወቅት አደጋው ያጋጠመው እጅግ መንፈሳዊ ወጣት ነበር። በደግነቱ፣ በሞቅታው እና በለጋስነቱ የሚታወቅ መሆኑን የገለጸው ማሰባሰቢያው፣ የሚሰበሰበው ገንዘብ ለቀብር ስነ-ስርዓት እና አስከሬኑን ወደ ሀገሩ ኢትዮጵያ ለመመለስ እንደሚውል አስታውቋል።
3 days ago
በፔሩ የቱሪስት አውሮፕላን ተከስክሶ 13 ሰዎች ሞቱ
ፔሩ ውስጥ ቱሪስቶችን ጭኖ ሲበርር የነበረ አነስተኛ አውሮፕላን ተከስክሶ፣ በውስጡ የነበሩት 13 ሰዎች በሙሉ ሕይወታቸው ማለፉን የአገሪቱ ባለሥልጣናት እና መገናኛ ብዙኃን ገለጹ።
‘ሴስና ካራቫን ሲ-208’ የተባለው አውሮፕላን ቅዳሜ ዕለት የተከሰከሰው ‘ናዝካ ላይንስ’ በተሰኘው አርኪኦሎጂ ስፍራ በኩል እየበረረ በነበረበት ወቅት ነው። አውሮፕላኑ 11 ተሳፋሪዎች እና ሁለት ፓይለቶች ይዞ ነበር።
ከተሳፋሪዎቹ መካከል ሁለት ጀርመናውያን፣ ሁለት የስፔን ዜጎች እና ሰባት ጣሊያናውያን ቱሪስቶች እንደነበሩ የፔሩ የመንግሥት የዜና ወኪል ዘግቧል። አደጋው የደረሰበት ምክንያት እስካሁን አልታወቀም።
በደቡባዊ ፔሩ የሚገኘው ‘ናዝካ ላይንስ’፣ በበረሃ አሸዋ ላይ የተሳሉ ጥንታዊ የእንስሳት ስዕሎች የሚታዩበት እና በዩኔስኮ የዓለም ቅርስነት የተመዘገበ ታዋቂ የቱሪስት ስፍራ መስህብ ነው።
ብዙውን ጊዜ ቱሪስቶች ስዕሎቹ ምን ያህል ስፋት ያለው ስፍራ ላይ እንዳረፉ ለመመልከት በአነስተኛ አውሮፕላኖች ይበራሉ
የፔሩ ፖሊስ አመራሩ ሜጀር ጆርጅ አንደራዴ "ከአደጋው አስከፊነት የተነሳ በሕይወት የተረፈ ሰው የለም። እስካሁን የአራት ሰዎችን አስከሬን አግኝተናል" ማለታቸውን ኤኤፍፒ ዘግቧል።
‘ፒስኮ’ በተባለው የፔሩ ከተማ ከሚገኝ አየር ማረፊያ የተነሳው አውሮፕላን የተከሰከሰው ፑዌብሎ ቪየሆ የተባለው ክልል ውስጥ ነው።
የዜና ወኪሉ ሮይተርስ ባወጣው አንድ ቪዲዮ ላይ የእሳት አደጋ ሠራተኞች ከስብርባሪዎች ጭስ የሚወጣበት የአደጋ ስፍራ ላይ ውሃ ሲረጩ ያሳያል።
‘ዴ ናስካ’ ግዛት አስተዳደር ባወጣው መግለጫ አውሮፕላኑ ‘ኤሮዲያና’ የተሰኘው የፔሩ የአገር ውስጥ አየር መንገድ ንብረት መሆኑን አስታውቋል።
አየር መንገዱ በበኩሉ ጉዳዩ "የሚመለከታቸው ባለሥልጣናት ከሚያወጧቸው መመሪያዎች ጋር በተጣጣመ መልኩ የበረራ መርሃ ግብሩን እንደሚገመግም" መግለጹን ሮይተርስ ዘግቧል።
ይህ ታዋቂ የቱሪስት መስህብ ባለፉት አስርት ዓመት ውስጥ ሌሎች የአውሮፕላን አደጋዎችንም አስተናግዷል።
በአውሮፓውያኑ 2022 አንድ አነስተኛ የቱሪስት አውሮፕላን በናዝካ ላይስ በኩል ሲበርር ተከስክሶ ሰባት ተሳፋሪዎች ሞተዋል።
2010 ላይ ደግሞ ሌላ የቱሪስት አውሮፕላን ወድቆ ተሳፍረው የነበሩ ስድስት ሰዎችን ገድሏል።
BBC
ፔሩ ውስጥ ቱሪስቶችን ጭኖ ሲበርር የነበረ አነስተኛ አውሮፕላን ተከስክሶ፣ በውስጡ የነበሩት 13 ሰዎች በሙሉ ሕይወታቸው ማለፉን የአገሪቱ ባለሥልጣናት እና መገናኛ ብዙኃን ገለጹ።
‘ሴስና ካራቫን ሲ-208’ የተባለው አውሮፕላን ቅዳሜ ዕለት የተከሰከሰው ‘ናዝካ ላይንስ’ በተሰኘው አርኪኦሎጂ ስፍራ በኩል እየበረረ በነበረበት ወቅት ነው። አውሮፕላኑ 11 ተሳፋሪዎች እና ሁለት ፓይለቶች ይዞ ነበር።
ከተሳፋሪዎቹ መካከል ሁለት ጀርመናውያን፣ ሁለት የስፔን ዜጎች እና ሰባት ጣሊያናውያን ቱሪስቶች እንደነበሩ የፔሩ የመንግሥት የዜና ወኪል ዘግቧል። አደጋው የደረሰበት ምክንያት እስካሁን አልታወቀም።
በደቡባዊ ፔሩ የሚገኘው ‘ናዝካ ላይንስ’፣ በበረሃ አሸዋ ላይ የተሳሉ ጥንታዊ የእንስሳት ስዕሎች የሚታዩበት እና በዩኔስኮ የዓለም ቅርስነት የተመዘገበ ታዋቂ የቱሪስት ስፍራ መስህብ ነው።
ብዙውን ጊዜ ቱሪስቶች ስዕሎቹ ምን ያህል ስፋት ያለው ስፍራ ላይ እንዳረፉ ለመመልከት በአነስተኛ አውሮፕላኖች ይበራሉ
የፔሩ ፖሊስ አመራሩ ሜጀር ጆርጅ አንደራዴ "ከአደጋው አስከፊነት የተነሳ በሕይወት የተረፈ ሰው የለም። እስካሁን የአራት ሰዎችን አስከሬን አግኝተናል" ማለታቸውን ኤኤፍፒ ዘግቧል።
‘ፒስኮ’ በተባለው የፔሩ ከተማ ከሚገኝ አየር ማረፊያ የተነሳው አውሮፕላን የተከሰከሰው ፑዌብሎ ቪየሆ የተባለው ክልል ውስጥ ነው።
የዜና ወኪሉ ሮይተርስ ባወጣው አንድ ቪዲዮ ላይ የእሳት አደጋ ሠራተኞች ከስብርባሪዎች ጭስ የሚወጣበት የአደጋ ስፍራ ላይ ውሃ ሲረጩ ያሳያል።
‘ዴ ናስካ’ ግዛት አስተዳደር ባወጣው መግለጫ አውሮፕላኑ ‘ኤሮዲያና’ የተሰኘው የፔሩ የአገር ውስጥ አየር መንገድ ንብረት መሆኑን አስታውቋል።
አየር መንገዱ በበኩሉ ጉዳዩ "የሚመለከታቸው ባለሥልጣናት ከሚያወጧቸው መመሪያዎች ጋር በተጣጣመ መልኩ የበረራ መርሃ ግብሩን እንደሚገመግም" መግለጹን ሮይተርስ ዘግቧል።
ይህ ታዋቂ የቱሪስት መስህብ ባለፉት አስርት ዓመት ውስጥ ሌሎች የአውሮፕላን አደጋዎችንም አስተናግዷል።
በአውሮፓውያኑ 2022 አንድ አነስተኛ የቱሪስት አውሮፕላን በናዝካ ላይስ በኩል ሲበርር ተከስክሶ ሰባት ተሳፋሪዎች ሞተዋል።
2010 ላይ ደግሞ ሌላ የቱሪስት አውሮፕላን ወድቆ ተሳፍረው የነበሩ ስድስት ሰዎችን ገድሏል።
BBC
3 days ago
u12a5u1295u12b3u1295 u1208u12d5u1208u1275 u1230u1295u1260u1275 u1260u1230u120bu121d u12a0u12f0u1228u1233u127du1201 u12a5u12ebu1208u127d u12e8u1218u120du12d5u120du1270 u12a0u12f5u1263u122bu1275 u12f0u1265u1228 u1230u120bu121d u1218u12f5u1283u1294u12d3u1208u121d u12abu1274u12f5u122bu120d u12e8u12a2u1275u12eeu1335u12eb u12a6u122du1276u12f6u12adu1235 u1270u12cbu1205u12f6 u1264u1270 u12adu122du1235u1272u12ebu1295 u12e8u12d5u1208u1271u1295 u1245u12f3u1234 u12a5u1293 u1235u1265u12a8u1270 u12c8u1295u130cu120d u1260u1240u1325u1273 u1225u122du132du1275 u1273u1235u1270u120bu120du134bu1208u127d - u121au1292u12ebu1356u120au1235 u121au1292u1236u1273 - u1210u121du120c u1373u136e u1240u1295, u1373u137bu1372u1370 (Aug 2 2026).","delight_ranges":[],"image_ranges":[],"inline_style_ranges":[],"aggregated_ranges":[],"ranges":[],"color_ranges":[]},"id":"UzpfSTEwMDA2NDc0Nzc3NTgyMjpWSzoxMDUxMDM2NTUxMjQwNzQx
እንኳን ለዕለት ሰንበት በሰላም አደረሳችሁ እያለች የመልዕልተ አድባራት ደብረ ሰላም መድኃኔዓለም ካቴድራል የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን የዕለቱን ቅዳሴ እና ስብከተ ወንጌል በቀጥታ ሥርጭት ታስተላልፋለች - ሚኒያፖሊስ ሚኒሶታ - ሐምሌ ፳፮ ቀን, ፳፻፲፰ (Aug 2 2026).
Sponsored by
Surafel
3 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የሚኒያፖሊስ ፖሊስ ዲፓርትመንት የጠፉ ሁለት ታዳጊ ሴቶችን አድራሻ ለማግኘት እንዲረዳው የህብረተሰቡን ትብብር እየጠየቀ ይገኛል። ሁለቱ ታዳጊዎች አብረው እንዳሉ ተገምቷል።
የመጀመሪያዋ ታዳጊ የ14 ዓመቷ ሪሃና ዑስማን ስትሆን፣ ከጁላይ 23 ጀምሮ የጠፋች መሆኗ ተነግሯል። ሪሃና ቁመቷ 5 ጫማ ከ 5 ኢንች፣ ክብደቷ 150 ፓውንድ ሲሆን፣ ቀይ ጸጉር እና ቡናማ አይን ያላት፣ እንዲሁም አፍንጫዋን እና ጆሮዋን የተበሳች ናት። ለመጨረሻ ጊዜ ስትታይ አረንጓዴ ሹራብ፣ እንዲሁም ከኋላው "Ed Hardy" የሚል ጽሁፍ ያለው ቡናማ ሱሪ ለብሳ ነበር። በተጨማሪም ሪሃና በአሁኑ ወቅት በየቀኑ መውሰድ ያለባትን እና ጥገኛ የሆነችበትን አስፈላጊ መድሃኒት እያገኘች እንዳልሆነ የፖሊስ ባለስልጣናት አሳስበዋል።
ሁለተኛዋ ታዳጊ የ15 ዓመቷ አይሻ አህመድ ከጁላይ 31 ጀምሮ የጠፋች ሲሆን፣ ፖሊስ አይሻ ከሪሃና ጋር አብራ እንዳለች ያምናል። አይሻ ቁመቷ 5 ጫማ ከ 6 ኢንች፣ ክብደቷ 156 ፓውንድ፣ እንዲሁም ጥቁር ጸጉር እና ቡናማ አይን ያላት ታዳጊ ናት።
ማንኛውም ግለሰብ ስለነዚህ ታዳጊዎች ያሉበት ቦታ መረጃ ካለው፣ የሚኒያፖሊስ ፖሊስ ዲፓርትመንትን በስልክ ቁጥር 612-348-2345 ወይም በአስቸኳይ ጊዜ ስልክ 911 በመደወል ጥቆማ እንዲሰጥ ፖሊስ ጥሪውን አስተላልፏል። #minnesota
የመጀመሪያዋ ታዳጊ የ14 ዓመቷ ሪሃና ዑስማን ስትሆን፣ ከጁላይ 23 ጀምሮ የጠፋች መሆኗ ተነግሯል። ሪሃና ቁመቷ 5 ጫማ ከ 5 ኢንች፣ ክብደቷ 150 ፓውንድ ሲሆን፣ ቀይ ጸጉር እና ቡናማ አይን ያላት፣ እንዲሁም አፍንጫዋን እና ጆሮዋን የተበሳች ናት። ለመጨረሻ ጊዜ ስትታይ አረንጓዴ ሹራብ፣ እንዲሁም ከኋላው "Ed Hardy" የሚል ጽሁፍ ያለው ቡናማ ሱሪ ለብሳ ነበር። በተጨማሪም ሪሃና በአሁኑ ወቅት በየቀኑ መውሰድ ያለባትን እና ጥገኛ የሆነችበትን አስፈላጊ መድሃኒት እያገኘች እንዳልሆነ የፖሊስ ባለስልጣናት አሳስበዋል።
ሁለተኛዋ ታዳጊ የ15 ዓመቷ አይሻ አህመድ ከጁላይ 31 ጀምሮ የጠፋች ሲሆን፣ ፖሊስ አይሻ ከሪሃና ጋር አብራ እንዳለች ያምናል። አይሻ ቁመቷ 5 ጫማ ከ 6 ኢንች፣ ክብደቷ 156 ፓውንድ፣ እንዲሁም ጥቁር ጸጉር እና ቡናማ አይን ያላት ታዳጊ ናት።
ማንኛውም ግለሰብ ስለነዚህ ታዳጊዎች ያሉበት ቦታ መረጃ ካለው፣ የሚኒያፖሊስ ፖሊስ ዲፓርትመንትን በስልክ ቁጥር 612-348-2345 ወይም በአስቸኳይ ጊዜ ስልክ 911 በመደወል ጥቆማ እንዲሰጥ ፖሊስ ጥሪውን አስተላልፏል። #minnesota
4 days ago
ከጋብቻ ውጭ የወለደችውን ልጅ በወላጆቿ ግቢ ውስጥ በድብቅ የቀበረችው ግለሰብ በእስራት ተቀጣች
በቡኖ በደሌ ዞን ጮራ ወረዳ ውስጥ ከጋብቻ ውጭ በጤና ተቋም በሰላም የተገላገለችውን ልጅ ወላጆቿ ግቢ ውስጥ በድብቅ የቀበረችው ግለሰብ በእስራት ተቀጥታለች።
የጮራ ወረዳ ፖሊስ ፅ/ቤት የወንጀል ምርመራ ክፍል ኃላፊ ኢንስፔክተር በለጠ ጉታ ለብስራት ሬዲዮ እንደገለጹት ተከሳሽ ሙሚሻ ሱልጣን የአስራ ዘጠኝ አመት ታዳጊ ወጣት መሆኗን ገልጸዋል።
ግንቦት 5 ቀን 2018 ዓ.ም ከምሽቱ ሶስት ሰዓት ላይ በሰላም ከጤና ጣቢያ ልጇን ተገላግላ ወደ ቤት ስትገባ ወላጆቿ ከጋብቻ ውጭ በመውለዷ ባደረሱባት ቁጣ ተፅዕኖ ስር ወድቃ በነጋታው አስር ሰዓት ላይ የወለደችውን ጨቅላ ወንድ ልጅ አፍና ገድላዋለች። አስክሬኑን ካርቶን ውስጥ ሸሽጋ በማቆየት ምሽት ሶስት ሰዓት ላይ ማንም ሳያያት ልትቀብር ስትል በአካባቢው ማህረሰብ ጥቆማ መሰረት በፖሊስ ቁጥጥር ስር ውላለች።
የአራስ ልጇን አስክሬን ወደ ደልቢ ጤና ጣቢያ በመላክ ተከሳሿ ላይ አስፈላጊውን የምርመራ መዝገብ በሰውና በሕክምና ማስረጃ በማጠናከር ለአቃቢ ህግ ተላልፏል። አቃቢ ህግም ከፖሊስ የቀረበውን መዝገብ ተመልክቶ በህፃን መግደል ወንጀል ክስ መስርቶባታል።
በአቃቢ ህግ የተመሰረተውን ክስ የተመለከተው የቡኖ በደሌ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ሀምሌ 20 ቀን 2018 ዓ.ም በዋለው ችሎት ተከሳሿ አስባ የፈፀመችው የወንጀል ድርጊት በመሆኑ በአስራ አምስት አመት እስራት እንድትቀጣ የወሰነባት መሆኑን ኢንስፔክተር በለጠ ጨምረው ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል።
Seledadotio
Seledadotio
በቡኖ በደሌ ዞን ጮራ ወረዳ ውስጥ ከጋብቻ ውጭ በጤና ተቋም በሰላም የተገላገለችውን ልጅ ወላጆቿ ግቢ ውስጥ በድብቅ የቀበረችው ግለሰብ በእስራት ተቀጥታለች።
የጮራ ወረዳ ፖሊስ ፅ/ቤት የወንጀል ምርመራ ክፍል ኃላፊ ኢንስፔክተር በለጠ ጉታ ለብስራት ሬዲዮ እንደገለጹት ተከሳሽ ሙሚሻ ሱልጣን የአስራ ዘጠኝ አመት ታዳጊ ወጣት መሆኗን ገልጸዋል።
ግንቦት 5 ቀን 2018 ዓ.ም ከምሽቱ ሶስት ሰዓት ላይ በሰላም ከጤና ጣቢያ ልጇን ተገላግላ ወደ ቤት ስትገባ ወላጆቿ ከጋብቻ ውጭ በመውለዷ ባደረሱባት ቁጣ ተፅዕኖ ስር ወድቃ በነጋታው አስር ሰዓት ላይ የወለደችውን ጨቅላ ወንድ ልጅ አፍና ገድላዋለች። አስክሬኑን ካርቶን ውስጥ ሸሽጋ በማቆየት ምሽት ሶስት ሰዓት ላይ ማንም ሳያያት ልትቀብር ስትል በአካባቢው ማህረሰብ ጥቆማ መሰረት በፖሊስ ቁጥጥር ስር ውላለች።
የአራስ ልጇን አስክሬን ወደ ደልቢ ጤና ጣቢያ በመላክ ተከሳሿ ላይ አስፈላጊውን የምርመራ መዝገብ በሰውና በሕክምና ማስረጃ በማጠናከር ለአቃቢ ህግ ተላልፏል። አቃቢ ህግም ከፖሊስ የቀረበውን መዝገብ ተመልክቶ በህፃን መግደል ወንጀል ክስ መስርቶባታል።
በአቃቢ ህግ የተመሰረተውን ክስ የተመለከተው የቡኖ በደሌ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ሀምሌ 20 ቀን 2018 ዓ.ም በዋለው ችሎት ተከሳሿ አስባ የፈፀመችው የወንጀል ድርጊት በመሆኑ በአስራ አምስት አመት እስራት እንድትቀጣ የወሰነባት መሆኑን ኢንስፔክተር በለጠ ጨምረው ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል።
Seledadotio
Seledadotio
4 days ago
የስዊድን ፖሊስ በሀገሩ ስለጠፉት ኢትዮጵያውያን ምን አለ?
#ethiopia | በስዊድን ጎተንበርግ በተካሄደው የ2026 የጎቲያ ካፕ የዓለም አቀፍ የታዳጊዎች እግር ኳስ ውድድር ላይ ከተሳተፉ በኋላ ደብዛቸው የጠፋው ኢትዮጵያውያን ታዳጊዎች በገዛ ፈቃዳቸው መሄዳቸውንና በጉዳዩ ላይ ምንም ዓይነት የወንጀል ወይም የሰው ህገወጥ ዝውውር ምልክት እንዳልተገኘ የስዊድን ፖሊስ አስታወቀ።
ከሀምሌ 12 እስከ 18 በተካሄደው በዚህ ውድድር ላይ ሲሳተፉ የቆዩትና ዕድሜያቸው ከ14 እስከ 17 ዓመት የሚሆኗቸው አብዛኞቹ ታዳጊዎች ከአንድ አዋቂ የቡድን መሪያቸው ጋር በድምሩ ወደ 20 የሚጠጉ የቡድኑ አባላት ያረፉበትን ትምህርት ቤት ለቀው የተሰወሩት በውድድሩ የመጨረሻ ቀን ነበር።
የውድድሩ አዘጋጆች ቡድኑ ማደሪያውን ያለ ምንም ቅድመ ማሳወቂያ ለቆ መሄዱን ከተረዱ በኋላ ወዲያውኑ ለፖሊስ ጥቆማ ማድረሳቸው ታውቋል።
የስዊድን ፖሊስ ከአስፈላጊ አካላት ጋር በመተባበር የቡድኑ አባላት ያሉበትን አድራሻ ለማወቅ ጥረቱን የቀጠለ ሲሆን እስካሁን ግን ምንም ዓይነት ሕገ-ወጥ ድርጊት ስለመፈጸሙ የሚያሳይ ማስረጃ እንደሌለ ገልጿል።
የኢትዮጵያው ክለብ ተወካይ ተጫዋቾቹ በደህና ሁኔታ ላይ እንደሚገኙና ከቤተሰቦቻቸው ጋር መገናኘታቸውን ለስዊድን መገናኛ ብዙኃን የገለጹ ቢሆንም፣ በአሁኑ ወቅት ያሉበትን ትክክለኛ ቦታ ወይም ወደ ኢትዮጵያ መመለሳቸውን ግን ከማረጋገጥ ተቆጥበዋል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ባወጣው መግለጫ በክስተቱ ማዘኑን ገልጾ ቡድኑ በራሱ መንገድ ባመቻቸው ጉዞ የተሳተፈ እንጂ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድንን ወክሎ እንዳልተጓዘ አብራርቷል።
አክሎም ህዝቡ ታዳጊዎቹ የብሔራዊ ቡድን አባላት እንደሆኑ አድርገው የሚያቀርቡ የተሳሳቱ ዘገባዎችን እንዳይቀበል አሳስቧል።
በያፌት ገ/ህይወት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#ethiopia | በስዊድን ጎተንበርግ በተካሄደው የ2026 የጎቲያ ካፕ የዓለም አቀፍ የታዳጊዎች እግር ኳስ ውድድር ላይ ከተሳተፉ በኋላ ደብዛቸው የጠፋው ኢትዮጵያውያን ታዳጊዎች በገዛ ፈቃዳቸው መሄዳቸውንና በጉዳዩ ላይ ምንም ዓይነት የወንጀል ወይም የሰው ህገወጥ ዝውውር ምልክት እንዳልተገኘ የስዊድን ፖሊስ አስታወቀ።
ከሀምሌ 12 እስከ 18 በተካሄደው በዚህ ውድድር ላይ ሲሳተፉ የቆዩትና ዕድሜያቸው ከ14 እስከ 17 ዓመት የሚሆኗቸው አብዛኞቹ ታዳጊዎች ከአንድ አዋቂ የቡድን መሪያቸው ጋር በድምሩ ወደ 20 የሚጠጉ የቡድኑ አባላት ያረፉበትን ትምህርት ቤት ለቀው የተሰወሩት በውድድሩ የመጨረሻ ቀን ነበር።
የውድድሩ አዘጋጆች ቡድኑ ማደሪያውን ያለ ምንም ቅድመ ማሳወቂያ ለቆ መሄዱን ከተረዱ በኋላ ወዲያውኑ ለፖሊስ ጥቆማ ማድረሳቸው ታውቋል።
የስዊድን ፖሊስ ከአስፈላጊ አካላት ጋር በመተባበር የቡድኑ አባላት ያሉበትን አድራሻ ለማወቅ ጥረቱን የቀጠለ ሲሆን እስካሁን ግን ምንም ዓይነት ሕገ-ወጥ ድርጊት ስለመፈጸሙ የሚያሳይ ማስረጃ እንደሌለ ገልጿል።
የኢትዮጵያው ክለብ ተወካይ ተጫዋቾቹ በደህና ሁኔታ ላይ እንደሚገኙና ከቤተሰቦቻቸው ጋር መገናኘታቸውን ለስዊድን መገናኛ ብዙኃን የገለጹ ቢሆንም፣ በአሁኑ ወቅት ያሉበትን ትክክለኛ ቦታ ወይም ወደ ኢትዮጵያ መመለሳቸውን ግን ከማረጋገጥ ተቆጥበዋል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ባወጣው መግለጫ በክስተቱ ማዘኑን ገልጾ ቡድኑ በራሱ መንገድ ባመቻቸው ጉዞ የተሳተፈ እንጂ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድንን ወክሎ እንዳልተጓዘ አብራርቷል።
አክሎም ህዝቡ ታዳጊዎቹ የብሔራዊ ቡድን አባላት እንደሆኑ አድርገው የሚያቀርቡ የተሳሳቱ ዘገባዎችን እንዳይቀበል አሳስቧል።
በያፌት ገ/ህይወት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
4 days ago
የቅዱሳን ይርጋለም እህት ሩት ይርጋለም የፖሊስን እርምጃ አደነቀች
#fastmereja I በቅርቡ በአሰቃቂ ሁኔታ ህይወቷ ያለፈው የቅዱሳን ይርጋለም እህት ሩት ይርጋለም፣ የአዲስ አበባ ፖሊስ የተጠረጠሩትን ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ለማዋል ባደረገው ፈጣንና የተቀናጀ ክትትል የተሰማትን ከፍተኛ ምስጋና ገለጸች።
ሩት በማህበራዊ ሚዲያ ባስተላለፈችው መልዕክት፣ የአዲስ አበባ ፖሊስ ባደረገው የጠበቀ ክትትል ተጠርጣሪዎቹ ሳይበተኑ እና ልብሳቸውንም ሳይቀይሩ በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ገልጻለች። ይህ ክስተት የአንድ ቤተሰብ ጉዳይ ብቻ ሳይሆን የጠቅላላው ህብረተሰብ ጉዳይ መሆኑን ያመለከተችው ሩት፣ መሰል አስቃቂ ድርጊቶች በሌሎች ቤተሰቦች ላይ እንዳይደገሙ ሲባል ለቅዱሳን ትክክለኛና ተመጣጣኝ ፍትህ እንዲሰጥ ጠይቃለች።
ህዝቡም ለጉዳዩ የሰጠውን ትኩረትና ያሳየውን አጋርነት በማመስገን፣ ፍትህ እስኪረጋገጥ ድረስ ህዝቡ ከጎናቸው እንዲቆም ጥሪዋን አስተላልፋለች።
#fastmereja I በቅርቡ በአሰቃቂ ሁኔታ ህይወቷ ያለፈው የቅዱሳን ይርጋለም እህት ሩት ይርጋለም፣ የአዲስ አበባ ፖሊስ የተጠረጠሩትን ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ለማዋል ባደረገው ፈጣንና የተቀናጀ ክትትል የተሰማትን ከፍተኛ ምስጋና ገለጸች።
ሩት በማህበራዊ ሚዲያ ባስተላለፈችው መልዕክት፣ የአዲስ አበባ ፖሊስ ባደረገው የጠበቀ ክትትል ተጠርጣሪዎቹ ሳይበተኑ እና ልብሳቸውንም ሳይቀይሩ በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ገልጻለች። ይህ ክስተት የአንድ ቤተሰብ ጉዳይ ብቻ ሳይሆን የጠቅላላው ህብረተሰብ ጉዳይ መሆኑን ያመለከተችው ሩት፣ መሰል አስቃቂ ድርጊቶች በሌሎች ቤተሰቦች ላይ እንዳይደገሙ ሲባል ለቅዱሳን ትክክለኛና ተመጣጣኝ ፍትህ እንዲሰጥ ጠይቃለች።
ህዝቡም ለጉዳዩ የሰጠውን ትኩረትና ያሳየውን አጋርነት በማመስገን፣ ፍትህ እስኪረጋገጥ ድረስ ህዝቡ ከጎናቸው እንዲቆም ጥሪዋን አስተላልፋለች።
Sponsored by
Surafel
4 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) በቅርቡ የህዝቡን ልብ በሀዘን የሰበረውንና በማህበራዊ ሚዲያ ከፍተኛ መነጋገሪያ የሆነውን የወጣቷ ቅዱሳን ይርጋለም አሰቃቂ ግድያን ተከትሎ፣ የሟች ታናሽ እህት እና የሚስ ወርልድ ኢትዮጵያ አክሊል ባለቤት ሩት ይርጋለም ለመጀመሪያ ጊዜ ዝምታዋን በመስበር ይፋዊ መግለጫ ሰጥታለች። ሩት በሰጠችው ስሜት ቀስቃሽና ጥልቅ መልዕክት ያዘለ መግለጫ፣ የወንጀሉን አሰቃቂነት፣ በፖሊስ የተደረገውን ክትትል እና የቀጣይ የፍትህ ሂደትን በተመለከተ ጠንካራ መልዕክት አስተላልፋለች።
ሩት በመግለጫዋ ዋነኛ ትኩረት ካደረገችባቸው ነጥቦች አንዱ የወንጀሉ ፈጻሚዎች ማንነት እና በሟች ላይ የደረሰው የክህደት መጠን ነው። የግድያው ዋነኛ ተጠርጣሪዎች የሟች ቅዱሳን እጅግ የቅርብ ጓደኛ እና የጓደኛዋ ፍቅረኛ መሆናቸውን ያረጋገጠችው ሩት፣ ድርጊቱን በቃላት ለመግለጽ የሚከብድ የጭካኔ ጥግ ስትል ኮንናዋለች። "የቅርብ ሰው ይቅርና ወዳጅ የማንለው ጠላት የማያደርገውን ተግባር እህቴ ላይ ፈጽመዋል" በማለት በቅርብ ወዳጅ የተፈጸመውን ይህንን አሰቃቂ ወንጀል በማህበረሰቡ ውስጥ ያለውን የመተማመን እሴት የሚንድ መሆኑን አብራርታለች።
በወንጀሉ ዙሪያ ፖሊስ ያደረገውን ክትትል በተመለከተ ሩት ከፍተኛ አድናቆትና ምስጋና አቅርባለች። የተጠርጣሪዎቹን ዱካ በመከታተል በቁጥጥር ስር ለማዋል የአዲስ አበባ ፖሊስ አባላት ያሳዩትን ከፍተኛ ቁርጠኝነት መስክራለች። "ልጆቹን ለመያዝ በተደረገው የተጠናከረ ስራ፣ ሌሊትና ቀን ልብስ እንኳ ሳይቀይሩ ከእኛ ጋር አብረው 'አይዟችሁ' እያሉ ለሰሩት ስራ በጣም አመሰግናለሁ" ስትል የጸጥታ አካላቱ የህዝብን ደህንነት ለማረጋገጥ ያደረጉትን ተጋድሎ አወድሳለች።
የቅዱሳን ሞት ከግለሰብ እና ከቤተሰብ ሀዘን ባለፈ አጠቃላይ የማህበረሰቡን የደህንነት ስጋት የሚያንጸባርቅ መሆኑን ሩት አበክራ ገልጻለች። ህብረተሰቡ በሀዘናቸው ጊዜ ከጎናቸው በመቆሙ ምስጋናዋን አቅርባ፣ "ይሄ የአንድ ሰው ጉዳይ ብቻ አይደለም፣ የሀገር ጉዳይ ነው" በማለት ወንጀሉን ሰፋ ባለ ሀገራዊ እና ማህበራዊ መነጽር እንዲታይ አድርጋለች።
"ዛሬ እኔ ቤት የመጣ ክፉ ሀዘን ነገ የናንተን ቤት ወይም የማንኛውንም ሰው ቤት እንዳያንኳኳ ትክክለኛው ፍትህ ሊሰጥ ይገባል" በማለት ያስጠነቀቀችው ሩት፣ የፍትህ ስርዓቱ በማያዳግም ሁኔታ ተገቢውን ቅጣት እንዲሰጥ አሳስባለች። በመጨረሻም መላው ህዝብ እና የሚመለከታቸው አካላት "ጀስቲስ ፎር ቅዱሳን" (ፍትህ ለቅዱሳን) በሚለው የፍትህ ጥያቄ ዙሪያ በመሰባሰብ ወንጀለኞቹ ትክክለኛውን ቅጣት እስኪያገኙ ድረስ ከጎናቸው እንዲቆሙ ጥሪዋን አስተላልፋለች።
ይህ የሩት ይርጋለም መግለጫ፣ በሀገሪቱ ውስጥ እየተበራከቱ የመጡትን አሰቃቂ የግድያና የክህደት ወንጀሎች በተመለከተ የፍትህ አካላት ጠንካራና አስተማሪ ርምጃ እንዲወስዱ ትልቅ ማሳሰቢያ የሰጠ ክሪቲካል ዘገባ ሆኖ አልፏል።
ሩት በመግለጫዋ ዋነኛ ትኩረት ካደረገችባቸው ነጥቦች አንዱ የወንጀሉ ፈጻሚዎች ማንነት እና በሟች ላይ የደረሰው የክህደት መጠን ነው። የግድያው ዋነኛ ተጠርጣሪዎች የሟች ቅዱሳን እጅግ የቅርብ ጓደኛ እና የጓደኛዋ ፍቅረኛ መሆናቸውን ያረጋገጠችው ሩት፣ ድርጊቱን በቃላት ለመግለጽ የሚከብድ የጭካኔ ጥግ ስትል ኮንናዋለች። "የቅርብ ሰው ይቅርና ወዳጅ የማንለው ጠላት የማያደርገውን ተግባር እህቴ ላይ ፈጽመዋል" በማለት በቅርብ ወዳጅ የተፈጸመውን ይህንን አሰቃቂ ወንጀል በማህበረሰቡ ውስጥ ያለውን የመተማመን እሴት የሚንድ መሆኑን አብራርታለች።
በወንጀሉ ዙሪያ ፖሊስ ያደረገውን ክትትል በተመለከተ ሩት ከፍተኛ አድናቆትና ምስጋና አቅርባለች። የተጠርጣሪዎቹን ዱካ በመከታተል በቁጥጥር ስር ለማዋል የአዲስ አበባ ፖሊስ አባላት ያሳዩትን ከፍተኛ ቁርጠኝነት መስክራለች። "ልጆቹን ለመያዝ በተደረገው የተጠናከረ ስራ፣ ሌሊትና ቀን ልብስ እንኳ ሳይቀይሩ ከእኛ ጋር አብረው 'አይዟችሁ' እያሉ ለሰሩት ስራ በጣም አመሰግናለሁ" ስትል የጸጥታ አካላቱ የህዝብን ደህንነት ለማረጋገጥ ያደረጉትን ተጋድሎ አወድሳለች።
የቅዱሳን ሞት ከግለሰብ እና ከቤተሰብ ሀዘን ባለፈ አጠቃላይ የማህበረሰቡን የደህንነት ስጋት የሚያንጸባርቅ መሆኑን ሩት አበክራ ገልጻለች። ህብረተሰቡ በሀዘናቸው ጊዜ ከጎናቸው በመቆሙ ምስጋናዋን አቅርባ፣ "ይሄ የአንድ ሰው ጉዳይ ብቻ አይደለም፣ የሀገር ጉዳይ ነው" በማለት ወንጀሉን ሰፋ ባለ ሀገራዊ እና ማህበራዊ መነጽር እንዲታይ አድርጋለች።
"ዛሬ እኔ ቤት የመጣ ክፉ ሀዘን ነገ የናንተን ቤት ወይም የማንኛውንም ሰው ቤት እንዳያንኳኳ ትክክለኛው ፍትህ ሊሰጥ ይገባል" በማለት ያስጠነቀቀችው ሩት፣ የፍትህ ስርዓቱ በማያዳግም ሁኔታ ተገቢውን ቅጣት እንዲሰጥ አሳስባለች። በመጨረሻም መላው ህዝብ እና የሚመለከታቸው አካላት "ጀስቲስ ፎር ቅዱሳን" (ፍትህ ለቅዱሳን) በሚለው የፍትህ ጥያቄ ዙሪያ በመሰባሰብ ወንጀለኞቹ ትክክለኛውን ቅጣት እስኪያገኙ ድረስ ከጎናቸው እንዲቆሙ ጥሪዋን አስተላልፋለች።
ይህ የሩት ይርጋለም መግለጫ፣ በሀገሪቱ ውስጥ እየተበራከቱ የመጡትን አሰቃቂ የግድያና የክህደት ወንጀሎች በተመለከተ የፍትህ አካላት ጠንካራና አስተማሪ ርምጃ እንዲወስዱ ትልቅ ማሳሰቢያ የሰጠ ክሪቲካል ዘገባ ሆኖ አልፏል።
4 days ago
የነገሌ አርሲ የፖሊስ አባል በፈራረሠ ቤት ተጥሎ በረሃብ ተዳክሞ የተገኘ ሕፃን አንስታ ጡታን በማጥባት ከሞት ታደገችው
በምዕራብ አርሲ ዞን ነገሌ አርሲ ወረዳ ቱሉ ቀበሌ በፈራረሠ ቤት ተጥሎና በረሐብ ምክንያት ተዳክሞ የተገኘን ሕፃን የተመለከቱ የአካባቢው ነዋሪዎች ለፖሊስ ጥቆማ ያደርጋሉ።
ጥቆማ ከደረሣቸው የነገሌ አርሲ ወረዳ ፖሊሶች መካከል ኢንስፔክተር ጉደቱ ኡሊ የተባለችው ገና ሕፃኑን ስታይ በረሐብ የተዳከመ መሆኑን አይታ ቶሎ ከመሬት አንስታ ጡታን በማጥባት ከሞት የታደገች መሆኑን ብስራት ሬዲዮ ሰምቷል።
ሐምሌ 19 ቀን 2018 ማንነቷ ለጊዜው ባልታወቀች እናት የተጣለው የሑለት ወር ሕፃን በባዶና በፈራረሰ ቤት ሲያለቅስ የሠሙ ሠዎች ለፖሊስ በሠጡት ጥቆማ ሕፃኑ በረሐብ የተዳከመ የነበረ ሲሆን በኢንስፔክተር ጉደቱ ኡሊ መልካም ተግባር ጡቷን በመጥባት ሊያገግም ችሏል።
የፖሊስ መኮንኗ በፈፀመችው መልካም የእናትነት ተግባር ያገገመው የሑለት ወር ሕፃን በጤና ተቋም የተመጣጠነ ምግብ አግኝቶ በሙሉ ጤንነት ላይ ይገኛል።
Seledadotio
Seledadotio
በምዕራብ አርሲ ዞን ነገሌ አርሲ ወረዳ ቱሉ ቀበሌ በፈራረሠ ቤት ተጥሎና በረሐብ ምክንያት ተዳክሞ የተገኘን ሕፃን የተመለከቱ የአካባቢው ነዋሪዎች ለፖሊስ ጥቆማ ያደርጋሉ።
ጥቆማ ከደረሣቸው የነገሌ አርሲ ወረዳ ፖሊሶች መካከል ኢንስፔክተር ጉደቱ ኡሊ የተባለችው ገና ሕፃኑን ስታይ በረሐብ የተዳከመ መሆኑን አይታ ቶሎ ከመሬት አንስታ ጡታን በማጥባት ከሞት የታደገች መሆኑን ብስራት ሬዲዮ ሰምቷል።
ሐምሌ 19 ቀን 2018 ማንነቷ ለጊዜው ባልታወቀች እናት የተጣለው የሑለት ወር ሕፃን በባዶና በፈራረሰ ቤት ሲያለቅስ የሠሙ ሠዎች ለፖሊስ በሠጡት ጥቆማ ሕፃኑ በረሐብ የተዳከመ የነበረ ሲሆን በኢንስፔክተር ጉደቱ ኡሊ መልካም ተግባር ጡቷን በመጥባት ሊያገግም ችሏል።
የፖሊስ መኮንኗ በፈፀመችው መልካም የእናትነት ተግባር ያገገመው የሑለት ወር ሕፃን በጤና ተቋም የተመጣጠነ ምግብ አግኝቶ በሙሉ ጤንነት ላይ ይገኛል።
Seledadotio
Seledadotio
4 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) 'እግረኛው' በተሰኘው የዩቲዩብ ቻናል የተለያዩ ግለሰቦችን ቃለ ምልልስ በማድረግ የሚታወቀው ጋዜጠኛ ተክለሀይማኖት አዳነ፣ እንዲሁም የሀገር መከላከያ ሰራዊት የደንብ ልብስ በመልበስ አከራካሪ መልዕክቶችን ሲያስተላልፍ የነበረው አበባየሁ ደሜ (አለማየሁ) በፌዴራል ፖሊስ ቁጥጥር ስር ዋሉ።
የፌዴራል ፖሊስ ጋዜጠኛ ተክለሀይማኖትን ዛሬ በፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አንደኛ የወንጀል ችሎት ያቀረበው ሲሆን፣ "ሀሰተኛ መረጃ በማሰራጨትና ፍትህን ለማዛባት በመሞከር" ወንጀል እንደጠረጠረው ለችሎቱ አስታውቋል። ፍርድ ቤቱም የፖሊስን የክስ መዝገብ ከመረመረ በኋላ፣ የቀረበለትን የጊዜ ቀጠሮ ጥያቄ በመቀበል ለሐምሌ 28 ቀን 2018 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል። በመሆኑም አቶ ተክለሀይማኖት እስከ ቀጠሮው ዕለት ድረስ በማረሚያ ቤት በእስር የሚቆይ ይሆናል።
የጋዜጠኛው በቁጥጥር ስር መዋል መነሻ ምክንያት በውል ባይታወቅም፣ በቅርቡ ከ'ፊንቴክ' (Fintech) የመኪና ማጭበርበር ጉዳይ ጋር በተያያዘ ክስ ከተመሰረተባቸው አርቲስቶች ጋር ያደረገውን ቃለ ምልልስ በሚዲያው በሁለት ክፍሎች ማሰራጨቱ ይታወሳል። በተጨማሪም የሀገር መከላከያ ሰራዊት ልብስ ለብሶ ከቀረበው ግለሰብ ጋር ያደረገው አነጋጋሪ ቃለ ምልልስ ለዚህ እስር መንስኤ ሊሆን እንደሚችል ቢገመትም፣ ጉዳዩ ከነዚሁ ስርጭቶች ጋር ይያያዝ አይያያዝ ዘ-ሐበሻ ማረጋገጥ አልቻለም።
በተያያዘ ዜና፣ በጋዜጠኛው ሚዲያ ላይ ቃለ ምልልስ የሰጠው ግለሰብም በቁጥጥር ስር መዋሉ ተገልጿል። የሀገር መከላከያ ሰራዊት አልባሳትን ያለአግባብ በመጠቀም በየማህበራዊ ሚዲያው የአንድነትና የፍቅር ሀሳብ ከማስተላለፍ ይልቅ የመከፋፈል ንግግሮችን እና አላስፈላጊ መልእክቶችን ሲያሰራጭ የነበረው አበባየሁ ደሜ በፖሊስ ተይዟል።
የፌዴራል ፖሊስ ጋዜጠኛ ተክለሀይማኖትን ዛሬ በፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አንደኛ የወንጀል ችሎት ያቀረበው ሲሆን፣ "ሀሰተኛ መረጃ በማሰራጨትና ፍትህን ለማዛባት በመሞከር" ወንጀል እንደጠረጠረው ለችሎቱ አስታውቋል። ፍርድ ቤቱም የፖሊስን የክስ መዝገብ ከመረመረ በኋላ፣ የቀረበለትን የጊዜ ቀጠሮ ጥያቄ በመቀበል ለሐምሌ 28 ቀን 2018 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል። በመሆኑም አቶ ተክለሀይማኖት እስከ ቀጠሮው ዕለት ድረስ በማረሚያ ቤት በእስር የሚቆይ ይሆናል።
የጋዜጠኛው በቁጥጥር ስር መዋል መነሻ ምክንያት በውል ባይታወቅም፣ በቅርቡ ከ'ፊንቴክ' (Fintech) የመኪና ማጭበርበር ጉዳይ ጋር በተያያዘ ክስ ከተመሰረተባቸው አርቲስቶች ጋር ያደረገውን ቃለ ምልልስ በሚዲያው በሁለት ክፍሎች ማሰራጨቱ ይታወሳል። በተጨማሪም የሀገር መከላከያ ሰራዊት ልብስ ለብሶ ከቀረበው ግለሰብ ጋር ያደረገው አነጋጋሪ ቃለ ምልልስ ለዚህ እስር መንስኤ ሊሆን እንደሚችል ቢገመትም፣ ጉዳዩ ከነዚሁ ስርጭቶች ጋር ይያያዝ አይያያዝ ዘ-ሐበሻ ማረጋገጥ አልቻለም።
በተያያዘ ዜና፣ በጋዜጠኛው ሚዲያ ላይ ቃለ ምልልስ የሰጠው ግለሰብም በቁጥጥር ስር መዋሉ ተገልጿል። የሀገር መከላከያ ሰራዊት አልባሳትን ያለአግባብ በመጠቀም በየማህበራዊ ሚዲያው የአንድነትና የፍቅር ሀሳብ ከማስተላለፍ ይልቅ የመከፋፈል ንግግሮችን እና አላስፈላጊ መልእክቶችን ሲያሰራጭ የነበረው አበባየሁ ደሜ በፖሊስ ተይዟል።
5 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) በአሜሪካ ቴክሳስ ግዛት ኦስቲን ከተማ በታዋቂው የአማዞን ኩባንያ ውስጥ በሶፍትዌር ኢንጂነርነት ሲሰራ የነበረው (ከዚህ ቀደም በኢንሳ ሰርቷል) ኢትዮጵያዊው ወጣት ያዴሳ እምሩ አጋ በኔቫዳ ግዛት በሚገኘው ታዋቂው 'ሌክ ታሆ' ሐይቅ ውስጥ ሰምጦ አሳዛኝ ህልፈተ ህይወት እንዳጋጠመው ትናንት በዘ-ሐበሻ ዜና መዘገባችን ይታወሳል። የካሊፎርኒያ ጋዜጦች ዛሬ ተጨማሪ መረጃዎችን ይዘው ወጥተዋል። የሰላሳ ሁለት ዓመቱ ወጣት ያዴሳ ወደ ስፍራው ያቀናው ከቅርብ ጓደኞቹ ጋር በመሆን መንፈሳዊ የቤተክርስቲያን ኮንፈረንስ ላይ ለመካፈል እንደነበር የቅርብ ሰዎቹ እና ቤተሰቦቹ በከፍተኛ ሀዘን ውስጥ ሆነው ገልጸዋል።
አደጋው የደረሰው ሰኞ ምሽት አካባቢ ሲሆን፣ የዋሾ ካውንቲ የሸሪፍ ጽህፈት ቤት ፖሊሶች እንደገለጹት ወጣቱ ድንጋያማ ወደሆኑት የሐይቁ ክፍሎች እየዋኘ ከሄደ በኋላ በድንገት ከውሃው ወለል በታች ጠፍቶ ሊሰምጥ ችሏል። በአካባቢው የነበሩ ሰዎች በፍጥነት ወደ ውሃው በመግባት ያዴሳን አውጥተው የመጀመሪያ እርዳታ (CPR) ያደረጉለት ቢሆንም፣ እንዲሁም የድንገተኛ አደጋ ህክምና ባለሙያዎች ቦታው ላይ ደርሰው ህይወቱን ለመታደግ ከፍተኛ ጥረት ቢያደርጉም በዚያው በስፍራው ህይወቱ ሊያልፍ መቻሉን ፖሊስ አረጋግጧል።
የያዴሳ ጓደኞች፣ ቤተሰቦች እና የቤተክርስቲያን አባላት ለቀብር ማስፈጸሚያ የሚሆን የገንዘብ ማሰባሰቢያ ያዘጋጁ ሲሆን፣ ወጣቱ እጅግ ትሁት፣ ፊቱ ሁልጊዜ በፈገግታ የተሞላ እና ለሰዎች አሳቢ እንደነበር መሰክረውለታል። እምነቱ በህይወቱ ውስጥ ትልቁን ስፍራ እንደሚይዝና ተፈጥሮን ማድነቅ እንዲሁም መጎብኘት ይወድ እንደነበር አስታውሰዋል። በአሁኑ ወቅት አስከሬኑን ወደ ትውልድ ሀገሩ ኢትዮጵያ ለመላክ እና በአሜሪካም ሆነ በሀገር ቤት ለሚደረገው የቀብር ስነ-ስርዓት የሚወጣውን ወጪ ለመሸፈን ማህበረሰቡ ርብርብ እያደረገ ይገኛል። ቀጣሪው የአማዞን ኩባንያም የተወሰነውን ወጪ ለመሸፈን ከቤተሰቦቹ ጋር አብሮ እየሰራ መሆኑ ታውቋል።
የአካባቢው ፖሊስ አደጋውን ድንገተኛ የመስመጥ አደጋ ብሎ የመዘገበው ቢሆንም፣ የዋሾ ካውንቲ የህክምና መርማሪዎች ቢሮ ምርመራው ገና ስላላለቀ ትክክለኛውን የሞት መንስኤ ይፋ አለማድረጉን አሳውቋል። የባለሙያዎቹ ሪፖርት ሙሉ በሙሉ ተጠናቆ ለመውጣት ከአስር እስከ አስራ ሁለት ሳምንታት ሊፈጅ እንደሚችል ተገልጿል። ይህ አሳዛኝ ክስተት የተፈጠረው፣ በዚሁ ተመሳሳይ ሐይቅ ውስጥ ከጥቂት ሳምንታት በፊት ሌላ ሰው በውሃ ውስጥ አደጋ አጋጥሞት ህይወቱ ማለፉ ከተሰማ በኋላ መሆኑ ታውቋል።
የጎ ፈንድ ሚ ሊንኩን ኮመንት ላይ አስቀምጠናል።
አደጋው የደረሰው ሰኞ ምሽት አካባቢ ሲሆን፣ የዋሾ ካውንቲ የሸሪፍ ጽህፈት ቤት ፖሊሶች እንደገለጹት ወጣቱ ድንጋያማ ወደሆኑት የሐይቁ ክፍሎች እየዋኘ ከሄደ በኋላ በድንገት ከውሃው ወለል በታች ጠፍቶ ሊሰምጥ ችሏል። በአካባቢው የነበሩ ሰዎች በፍጥነት ወደ ውሃው በመግባት ያዴሳን አውጥተው የመጀመሪያ እርዳታ (CPR) ያደረጉለት ቢሆንም፣ እንዲሁም የድንገተኛ አደጋ ህክምና ባለሙያዎች ቦታው ላይ ደርሰው ህይወቱን ለመታደግ ከፍተኛ ጥረት ቢያደርጉም በዚያው በስፍራው ህይወቱ ሊያልፍ መቻሉን ፖሊስ አረጋግጧል።
የያዴሳ ጓደኞች፣ ቤተሰቦች እና የቤተክርስቲያን አባላት ለቀብር ማስፈጸሚያ የሚሆን የገንዘብ ማሰባሰቢያ ያዘጋጁ ሲሆን፣ ወጣቱ እጅግ ትሁት፣ ፊቱ ሁልጊዜ በፈገግታ የተሞላ እና ለሰዎች አሳቢ እንደነበር መሰክረውለታል። እምነቱ በህይወቱ ውስጥ ትልቁን ስፍራ እንደሚይዝና ተፈጥሮን ማድነቅ እንዲሁም መጎብኘት ይወድ እንደነበር አስታውሰዋል። በአሁኑ ወቅት አስከሬኑን ወደ ትውልድ ሀገሩ ኢትዮጵያ ለመላክ እና በአሜሪካም ሆነ በሀገር ቤት ለሚደረገው የቀብር ስነ-ስርዓት የሚወጣውን ወጪ ለመሸፈን ማህበረሰቡ ርብርብ እያደረገ ይገኛል። ቀጣሪው የአማዞን ኩባንያም የተወሰነውን ወጪ ለመሸፈን ከቤተሰቦቹ ጋር አብሮ እየሰራ መሆኑ ታውቋል።
የአካባቢው ፖሊስ አደጋውን ድንገተኛ የመስመጥ አደጋ ብሎ የመዘገበው ቢሆንም፣ የዋሾ ካውንቲ የህክምና መርማሪዎች ቢሮ ምርመራው ገና ስላላለቀ ትክክለኛውን የሞት መንስኤ ይፋ አለማድረጉን አሳውቋል። የባለሙያዎቹ ሪፖርት ሙሉ በሙሉ ተጠናቆ ለመውጣት ከአስር እስከ አስራ ሁለት ሳምንታት ሊፈጅ እንደሚችል ተገልጿል። ይህ አሳዛኝ ክስተት የተፈጠረው፣ በዚሁ ተመሳሳይ ሐይቅ ውስጥ ከጥቂት ሳምንታት በፊት ሌላ ሰው በውሃ ውስጥ አደጋ አጋጥሞት ህይወቱ ማለፉ ከተሰማ በኋላ መሆኑ ታውቋል።
የጎ ፈንድ ሚ ሊንኩን ኮመንት ላይ አስቀምጠናል።
5 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በይፋዊ መግለጫቸው በተያያዘው ግህግ.jpeg ሰነድ ላይ) እንዳስታወቁት፣ 'የሰላም ቦርድ' ሀማስን ጨምሮ በጋዛ የሚገኙ ሁሉንም ታጣቂ ቡድኖች ሙሉ በሙሉ ትጥቅ ለማስፈታት የሚያስችል ታሪካዊ ስምምነት ላይ ደርሷል። ይህ ስምምነት ዘላቂ ሰላም እና ደህንነትን ለማረጋገጥ የተወሰደ እጅግ ትልቅ እና ወሳኝ እርምጃ መሆኑን ፕሬዝዳንቱ ገልጸዋል።
ስምምነቱ ጋዛ ከሰላም ቦርዱ ጋር በቅርበት በመስራት የፍልስጤምን ህዝብ በሚያግዝ አዲስ የፍልስጤም መንግስት እንድትተዳደር የሚያስችል ወሳኝ ምዕራፍ ነው። በሌላ በኩል ደግሞ ጋዛ ዳግም የሽብር ጥቃቶች መነሻ መሆኗ ስለሚያበቃ፣ እስራኤል የሚገባትን ደህንነት እንደምታገኝ በመግለጫው ተጠቁሟል። ይህ እርምጃ የትራምፕን 'ባለ 20-ነጥብ የሰላም እቅድ' ተግባራዊ ለማድረግ የተመዘገበ ትልቅ ስኬት መሆኑም ተብራርቷል።
የስምምነቱ ትግበራ በጥንቃቄ በተዋቀሩ ደረጃዎች የሚከናወን ይሆናል። የትጥቅ ማስፈታት ሂደቱ ሲጠናቀቅ የእስራኤል ጦር ከጋዛ የሚወጣ ሲሆን፣ ዓለም አቀፍ የማረጋጋት ኃይል ከአዲሱ የፍልስጤም ፖሊስ ኃይል ጋር በመተባበር የጋዛን እና የጎረቤቶቿን ነዋሪዎች ደህንነት የማረጋገጥ ኃላፊነት ይወስዳል።
ፕሬዝዳንት ትራምፕ መግለጫቸውን ሲቀጥሉ ከአንድ ዓመት በፊት ከነበረው አውዳሚ ጦርነት፣ ከባድ ሰብዓዊ ቀውስ እና ታጋቾች በጭካኔ በተያዙበት ሁኔታ አንጻር ሲታይ ዛሬ ላይ ታሪካዊ መሻሻል መታየቱን አውስተው፣ አሁንም ግን ብዙ ሊሰሩ የሚገባቸው ስራዎች መኖራቸውን አሳስበዋል። ለዚህ ታሪካዊ ስኬት መገኘት ከፍተኛ ጥረት ላደረጉት አሸማጋይ ሀገራት ማለትም ለግብፅ፣ ለኳታር እና ለቱርክ፣ እንዲሁም ያለመታከት ለሰራው የራሳቸው የልዑካን ቡድን የላቀ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
በጥቅምት 7 ከጋዛ የተነሳው ስጋት ዳግም እራሱን እንዳይገነባ ጥብቅ አቋም የተያዘበት ይህ ስምምነት፣ ጋዛን በመጨረሻ ህዝቧን ለሚያገለግል አዲስ የፍልስጤም መንግስት የሚያስረክብ መሆኑ ተረጋግጧል። በመጨረሻም ፕሬዝዳንት ትራምፕ ማንም ሊሳካ አይችልም ተብሎ ይታሰብ በነበረው በዚህ አስደናቂ እድገት ለሁሉም የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት በማስተላለፍ መግለጫቸውን አጠናቀዋል።
ስምምነቱ ጋዛ ከሰላም ቦርዱ ጋር በቅርበት በመስራት የፍልስጤምን ህዝብ በሚያግዝ አዲስ የፍልስጤም መንግስት እንድትተዳደር የሚያስችል ወሳኝ ምዕራፍ ነው። በሌላ በኩል ደግሞ ጋዛ ዳግም የሽብር ጥቃቶች መነሻ መሆኗ ስለሚያበቃ፣ እስራኤል የሚገባትን ደህንነት እንደምታገኝ በመግለጫው ተጠቁሟል። ይህ እርምጃ የትራምፕን 'ባለ 20-ነጥብ የሰላም እቅድ' ተግባራዊ ለማድረግ የተመዘገበ ትልቅ ስኬት መሆኑም ተብራርቷል።
የስምምነቱ ትግበራ በጥንቃቄ በተዋቀሩ ደረጃዎች የሚከናወን ይሆናል። የትጥቅ ማስፈታት ሂደቱ ሲጠናቀቅ የእስራኤል ጦር ከጋዛ የሚወጣ ሲሆን፣ ዓለም አቀፍ የማረጋጋት ኃይል ከአዲሱ የፍልስጤም ፖሊስ ኃይል ጋር በመተባበር የጋዛን እና የጎረቤቶቿን ነዋሪዎች ደህንነት የማረጋገጥ ኃላፊነት ይወስዳል።
ፕሬዝዳንት ትራምፕ መግለጫቸውን ሲቀጥሉ ከአንድ ዓመት በፊት ከነበረው አውዳሚ ጦርነት፣ ከባድ ሰብዓዊ ቀውስ እና ታጋቾች በጭካኔ በተያዙበት ሁኔታ አንጻር ሲታይ ዛሬ ላይ ታሪካዊ መሻሻል መታየቱን አውስተው፣ አሁንም ግን ብዙ ሊሰሩ የሚገባቸው ስራዎች መኖራቸውን አሳስበዋል። ለዚህ ታሪካዊ ስኬት መገኘት ከፍተኛ ጥረት ላደረጉት አሸማጋይ ሀገራት ማለትም ለግብፅ፣ ለኳታር እና ለቱርክ፣ እንዲሁም ያለመታከት ለሰራው የራሳቸው የልዑካን ቡድን የላቀ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
በጥቅምት 7 ከጋዛ የተነሳው ስጋት ዳግም እራሱን እንዳይገነባ ጥብቅ አቋም የተያዘበት ይህ ስምምነት፣ ጋዛን በመጨረሻ ህዝቧን ለሚያገለግል አዲስ የፍልስጤም መንግስት የሚያስረክብ መሆኑ ተረጋግጧል። በመጨረሻም ፕሬዝዳንት ትራምፕ ማንም ሊሳካ አይችልም ተብሎ ይታሰብ በነበረው በዚህ አስደናቂ እድገት ለሁሉም የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት በማስተላለፍ መግለጫቸውን አጠናቀዋል።
Sponsored by
Surafel
5 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ህገ-መንግስት ከጸደቀ 30 ዓመታት ቢቆጠሩም፣ ሀገሪቱ አሁንም የሰዎችን ህይወት ከሚቀጥፉ፣ ማህበረሰብን ከሚያፈናቅሉ እና የህዝብን አመኔታ ከሚሸረሽሩ ተደጋጋሚ ግጭቶች መላቀቅ አልቻለችም። አብዛኛዎቹ ሰዎች ለእነዚህ ችግሮች የብሔር ወይም የፖለቲካ ፉክክርን በዋነኛነት ቢወቅሱም፣ የፖለቲካ ትንታኔዎች ግን ዋነኛው እና ስር የሰደደው ችግር የፌደራል እና የክልል መንግስታት የጸጥታ ኃላፊነት ድንበር በህገ-መንግስቱ ላይ በግልጽ አለመቀመጡ መሆኑን ያመላክታሉ።
ይህ ግልጽነት የጎደለው አሰራር "የተበታተነ ሉዓላዊነት" ፈጥሯል። ይህም ማለት የተለያዩ የመንግስት እርከኖች በተደራረበ ህጋዊ ስልጣን እና እርስ በርስ በሚፎካከር ፖለቲካዊ ፍላጎት የጸጥታ ኃይልን ያዛሉ። በዚህም ምክንያት የፌደራል እና የክልል የጸጥታ መዋቅሮች ተደጋግፈው ከመስራት ይልቅ፣ አንዳንዴ በትይዩ አልያም በፉክክር መንፈስ ሲንቀሳቀሱ ይታያሉ፤ ይህም ግጭትን ለመከላከል የሚደረገውን ጥረት አወሳስቦታል።
የዚህ አጣብቂኝ መነሻ ያለው እ.ኤ.አ. በ1995 በጸደቀው የኢትዮጵያ ህገ-መንግስት ውስጥ ነው። ህገ-መንግስቱ የሀገር መከላከያ እና የፌደራል ፖሊስን ኃላፊነት ለፌደራል መንግስቱ በአንቀጽ 51(6) ስር ሲሰጥ፣ በሌላ በኩል ደግሞ ክልሎች የራሳቸውን ፖሊስ ኃይል እንዲያቋቁሙ እና ጸጥታ እንዲያስከብሩ በአንቀጽ 52(2)(g) ላይ ስልጣን ይሰጣቸዋል። ይህ ድንጋጌ የክልሎችን ራስን በራስ የማስተዳደር መብት እና የሀገርን አንድነት ለማመጣጠን የታለመ ቢሆንም፣ የክልል የፖሊስ ስልጣን የት ላይ ያበቃል የፌደራል የጸጥታ ኃላፊነትስ የት ይጀምራል ለሚለው መሰረታዊ ጥያቄ ምላሽ ሳይሰጥ ቀርቷል።
በዚህም ምክንያት ሁለት ተቋማዊ ድክመቶች ተፈጥረዋል። የመጀመሪያው፣ ክልሎች የተሰጣቸውን የፖሊስ ኃይል የማቋቋም መብት በመጠቀም ከመደበኛ የፖሊስ ግዳጅ ባለፈ ወታደራዊ ቅርጽ እና ትጥቅ ያላቸውን የክልል ልዩ ኃይሎችን ማቋቋማቸው ነው። ሁለተኛው ደግሞ፣ በክልሎች መካከል የሚነሱ የድንበር እና የማንነት ጥያቄዎችን የሚፈታ ጠንካራ ተቋማዊ አሰራር ባለመኖሩ የክልል ፖሊስ ተቋማት የፖለቲካው አካል በመሆን ግጭቶችን ከማብረድ ይልቅ ተሳታፊ ወደ መሆን መሸጋገራቸው ነው።
ህገ-መንግስታዊ ክፍተት ብቻውን ብጥብጥ አያመጣም። ነገር ግን ፖለቲከኞች የጸጥታ ኃላፊነቶች በተደራረቡበት ስርዓት ውስጥ ሲንቀሳቀሱ አደገኛ ይሆናል። በኢትዮጵያ፣ አንዱ የመንግስት እርከን ለራሱ ደህንነት ሲል የሚወስደው ራስን የመከላከል እርምጃ፣ በሌላው ወገን እንደ ትንኮሳ እና ለጥቃት እንደመዘጋጀት ይቆጠራል።
ይህ ተለዋዋጭ ሁኔታ በሚያዝያ 2015 ዓ.ም. የፌደራል መንግስት የክልል ልዩ ኃይሎችን መልሶ ለማደራጀት በወሰደው እርምጃ ወቅት በግልጽ ታይቷል። መንግስት እርምጃውን የተዋሃደ ሀገራዊ የጸጥታ መዋቅር ለመገንባት ያለመ መሆኑን ቢገልጽም፣ በተለይም በአማራ ክልል ከፍተኛ ፖለቲካዊ ተቃውሞን እና ቀጣይነት ያለውን ግጭት አስከትሏል። ይህ የሚያሳየው፣ የክልል መንግስታት የጸጥታ ተቋሞቻቸውን እንደ ህገ-መንግስታዊ የራስ ገዝ አስተዳደር መገለጫ አድርገው በሚያዩበት ፌደራላዊ ስርዓት ውስጥ፣ ኃይልን ማዕከላዊ ለማድረግ የሚደረግ ማንኛውም ሙከራ እንደ ፖለቲካዊ ጣልቃ ገብነት እንደሚቆጠር ነው።
መዋቅራዊ መፍትሄዎች፡ ኃይልን ብቻ ሳይሆን ህጉን ማስተካከል
የኢትዮጵያን ተደጋጋሚ የጸጥታ ቀውሶች በዘላቂነት ለመፍታት የተለያዩ መዋቅራዊ ማሻሻያዎችን ማድረግ የግድ ይላል። በቅድሚያ በአንቀጽ 51 እና በአንቀጽ 52 መካከል ያለውን የፌደራል እና የክልል የጸጥታ ኃላፊነቶች ግንኙነት በግልጽ በማብራራት የፌደራል መንግስት በምን ዓይነት ሁኔታዎች ውስጥ ጣልቃ መግባት እንዳለበት ህጋዊ ድንበር ሊቀመጥ ይገባል። በተጨማሪም የክልልን ራስን በራስ የማስተዳደር መብት በማይጋፋ መልኩ፣ መረጃ የሚለዋወጡበት እና ግጭቶች ወደ ጦርነት ከማምራታቸው በፊት የሚፈቱበት ቋሚ የፌደራል እና የክልል የጸጥታ ማስተባበሪያ መዋቅር መገንባት ያስፈልጋል።
በሌላ በኩል የፖሊስ ተቋማት ከፖለቲካ ወገንተኝነት የጸዱ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ እና በፖለቲካ የተነሳሱ የጸጥታ ጥሰቶችን የሚመረምር ገለልተኛ የቁጥጥር አካል በማቋቋም ተቋማዊ ተጠያቂነትን ማረጋገጥ ወሳኝ እርምጃ ነው። እንዲሁም የክልል ፖሊሶች ለክልል ፖለቲካዊ ፍላጎቶች ሳይሆን ለህገ-መንግስቱ እና ለህግ የበላይነት ታማኝ የሚሆኑበትን የጋራ ስልጠና እና ኦፕሬሽናል መርሆች በመተግበር የጋራ ፕሮፌሽናል አስተምህሮ ማዳበር ይገባል።
የኢትዮጵያ ተደጋጋሚ የጸጥታ ቀውሶች የሚያሳዩት "ህገ-መንግስታዊ ንድፍ ልክ እንደ ፖለቲካዊ አመራር ሁሉ እጅግ ወሳኝ መሆኑን" ነው። ዘላቂ ሰላም ጊዜያዊ ተኩስ አቁምን ወይም ወቅታዊ የጸጥታ ዘመቻዎችን ብቻ ተመርኩዞ ሊመጣ አይችልም። የኢትዮጵያ ማዕከላዊ ጥያቄ የጸጥታ ማሻሻያ ያስፈልጋል ወይ የሚለው ሳይሆን፣ ማሻሻያው የችግሩን ውጫዊ ምልክቶች ብቻ ሳይሆን ተቋማዊ እና ህገ-መንግስታዊ ስር-መሰረቱን ይፈታል ወይ የሚለው ነው።
ይህ ግልጽነት የጎደለው አሰራር "የተበታተነ ሉዓላዊነት" ፈጥሯል። ይህም ማለት የተለያዩ የመንግስት እርከኖች በተደራረበ ህጋዊ ስልጣን እና እርስ በርስ በሚፎካከር ፖለቲካዊ ፍላጎት የጸጥታ ኃይልን ያዛሉ። በዚህም ምክንያት የፌደራል እና የክልል የጸጥታ መዋቅሮች ተደጋግፈው ከመስራት ይልቅ፣ አንዳንዴ በትይዩ አልያም በፉክክር መንፈስ ሲንቀሳቀሱ ይታያሉ፤ ይህም ግጭትን ለመከላከል የሚደረገውን ጥረት አወሳስቦታል።
የዚህ አጣብቂኝ መነሻ ያለው እ.ኤ.አ. በ1995 በጸደቀው የኢትዮጵያ ህገ-መንግስት ውስጥ ነው። ህገ-መንግስቱ የሀገር መከላከያ እና የፌደራል ፖሊስን ኃላፊነት ለፌደራል መንግስቱ በአንቀጽ 51(6) ስር ሲሰጥ፣ በሌላ በኩል ደግሞ ክልሎች የራሳቸውን ፖሊስ ኃይል እንዲያቋቁሙ እና ጸጥታ እንዲያስከብሩ በአንቀጽ 52(2)(g) ላይ ስልጣን ይሰጣቸዋል። ይህ ድንጋጌ የክልሎችን ራስን በራስ የማስተዳደር መብት እና የሀገርን አንድነት ለማመጣጠን የታለመ ቢሆንም፣ የክልል የፖሊስ ስልጣን የት ላይ ያበቃል የፌደራል የጸጥታ ኃላፊነትስ የት ይጀምራል ለሚለው መሰረታዊ ጥያቄ ምላሽ ሳይሰጥ ቀርቷል።
በዚህም ምክንያት ሁለት ተቋማዊ ድክመቶች ተፈጥረዋል። የመጀመሪያው፣ ክልሎች የተሰጣቸውን የፖሊስ ኃይል የማቋቋም መብት በመጠቀም ከመደበኛ የፖሊስ ግዳጅ ባለፈ ወታደራዊ ቅርጽ እና ትጥቅ ያላቸውን የክልል ልዩ ኃይሎችን ማቋቋማቸው ነው። ሁለተኛው ደግሞ፣ በክልሎች መካከል የሚነሱ የድንበር እና የማንነት ጥያቄዎችን የሚፈታ ጠንካራ ተቋማዊ አሰራር ባለመኖሩ የክልል ፖሊስ ተቋማት የፖለቲካው አካል በመሆን ግጭቶችን ከማብረድ ይልቅ ተሳታፊ ወደ መሆን መሸጋገራቸው ነው።
ህገ-መንግስታዊ ክፍተት ብቻውን ብጥብጥ አያመጣም። ነገር ግን ፖለቲከኞች የጸጥታ ኃላፊነቶች በተደራረቡበት ስርዓት ውስጥ ሲንቀሳቀሱ አደገኛ ይሆናል። በኢትዮጵያ፣ አንዱ የመንግስት እርከን ለራሱ ደህንነት ሲል የሚወስደው ራስን የመከላከል እርምጃ፣ በሌላው ወገን እንደ ትንኮሳ እና ለጥቃት እንደመዘጋጀት ይቆጠራል።
ይህ ተለዋዋጭ ሁኔታ በሚያዝያ 2015 ዓ.ም. የፌደራል መንግስት የክልል ልዩ ኃይሎችን መልሶ ለማደራጀት በወሰደው እርምጃ ወቅት በግልጽ ታይቷል። መንግስት እርምጃውን የተዋሃደ ሀገራዊ የጸጥታ መዋቅር ለመገንባት ያለመ መሆኑን ቢገልጽም፣ በተለይም በአማራ ክልል ከፍተኛ ፖለቲካዊ ተቃውሞን እና ቀጣይነት ያለውን ግጭት አስከትሏል። ይህ የሚያሳየው፣ የክልል መንግስታት የጸጥታ ተቋሞቻቸውን እንደ ህገ-መንግስታዊ የራስ ገዝ አስተዳደር መገለጫ አድርገው በሚያዩበት ፌደራላዊ ስርዓት ውስጥ፣ ኃይልን ማዕከላዊ ለማድረግ የሚደረግ ማንኛውም ሙከራ እንደ ፖለቲካዊ ጣልቃ ገብነት እንደሚቆጠር ነው።
መዋቅራዊ መፍትሄዎች፡ ኃይልን ብቻ ሳይሆን ህጉን ማስተካከል
የኢትዮጵያን ተደጋጋሚ የጸጥታ ቀውሶች በዘላቂነት ለመፍታት የተለያዩ መዋቅራዊ ማሻሻያዎችን ማድረግ የግድ ይላል። በቅድሚያ በአንቀጽ 51 እና በአንቀጽ 52 መካከል ያለውን የፌደራል እና የክልል የጸጥታ ኃላፊነቶች ግንኙነት በግልጽ በማብራራት የፌደራል መንግስት በምን ዓይነት ሁኔታዎች ውስጥ ጣልቃ መግባት እንዳለበት ህጋዊ ድንበር ሊቀመጥ ይገባል። በተጨማሪም የክልልን ራስን በራስ የማስተዳደር መብት በማይጋፋ መልኩ፣ መረጃ የሚለዋወጡበት እና ግጭቶች ወደ ጦርነት ከማምራታቸው በፊት የሚፈቱበት ቋሚ የፌደራል እና የክልል የጸጥታ ማስተባበሪያ መዋቅር መገንባት ያስፈልጋል።
በሌላ በኩል የፖሊስ ተቋማት ከፖለቲካ ወገንተኝነት የጸዱ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ እና በፖለቲካ የተነሳሱ የጸጥታ ጥሰቶችን የሚመረምር ገለልተኛ የቁጥጥር አካል በማቋቋም ተቋማዊ ተጠያቂነትን ማረጋገጥ ወሳኝ እርምጃ ነው። እንዲሁም የክልል ፖሊሶች ለክልል ፖለቲካዊ ፍላጎቶች ሳይሆን ለህገ-መንግስቱ እና ለህግ የበላይነት ታማኝ የሚሆኑበትን የጋራ ስልጠና እና ኦፕሬሽናል መርሆች በመተግበር የጋራ ፕሮፌሽናል አስተምህሮ ማዳበር ይገባል።
የኢትዮጵያ ተደጋጋሚ የጸጥታ ቀውሶች የሚያሳዩት "ህገ-መንግስታዊ ንድፍ ልክ እንደ ፖለቲካዊ አመራር ሁሉ እጅግ ወሳኝ መሆኑን" ነው። ዘላቂ ሰላም ጊዜያዊ ተኩስ አቁምን ወይም ወቅታዊ የጸጥታ ዘመቻዎችን ብቻ ተመርኩዞ ሊመጣ አይችልም። የኢትዮጵያ ማዕከላዊ ጥያቄ የጸጥታ ማሻሻያ ያስፈልጋል ወይ የሚለው ሳይሆን፣ ማሻሻያው የችግሩን ውጫዊ ምልክቶች ብቻ ሳይሆን ተቋማዊ እና ህገ-መንግስታዊ ስር-መሰረቱን ይፈታል ወይ የሚለው ነው።
6 days ago
ይሄን ምስኪን ምን አድርግ ነው የምትሉት?
#ethiopia | የናቲ ገጠመኝ በግለሰብ ደረጃ የተፈጸመ ቅጥ አልባ ድርጊት ብቻ ሳይሆን በአሁኑ ወቅት በማህበራዊ ሚዲያ ላይ "እይታን" ለመቃረም ሲባል የሚደረግ የዘመኑ ልክፍት ነው።
ይህ ድርጊት ከቀልድነት አልፎ በሰዎች ሰላማዊ ህይወት ላይ የሚፈጸም ጥቃት ነው!
በመሠረቱ ፕራንክ የሚሉት ነገር ለዛ ቢስ ጨዋታ ነው ነገር ግን ፤ ይሁን ይደረግ ከተባለም (አድራጊውንም ሆነ ተደራጊውን) መጨረሻው የማያሳቅቅ እና የሰዎችን ስሜት የማይጎዳ መሆን ይገበዋል፤ አሁን አሁን ግን ሰዎችን ማዋከብ፣ ማስደንገጥ እና ስነ-ልቦናዊ ጫና ማድረስ እንደ መዝናኛ እየተቆጠረ ነው።
የናቲ ድንጋጤ እና ፊቱ ላይ ይነበብ የነበረው ጭንቀት ለነሱ "ጥሩ የቲክቶክ ቪዲዮ" ሲሆን፣ ለሱ ግን ትርጉሙ ሌላ ነው።
ሌላው የደንብ ልብስን አላግባብ መጠቀምስ ይቻላል ወይ?
አንደኛው ግለሰብ የፖሊስ ልብስ(የሚመስል) ለብሶ መምጣቱ ድርጊቱን ከስነ-ምግባር ግድፈት አልፎ ከባድ የህግ ጥሰት ያደርገዋል።
ዜጎች በጸጥታ አስከባሪዎች ላይ ሊኖራቸው የሚገባውን እምነት የሚሸረሽር እና የመንግስትን የደንብ ልብስ ለግል የሶሻል ሚዲያ ትርፍ ማዋረድ ነው።
የሰውን ልጅ ሰላም ነስቶ የሚገኝ ላይክ ዋጋው ስንት ነው?
መፍትሄው እና መማር ያለብን እሴት
፣ ከዚህ ሁሉ ጫጫታ እና የሰዎችን ክብር ከሚረግጥ አዝማሚያ ወጥተን ሰውን በማክበር ረገድ እንድናስብ ያስፈልጋል።
ጥበብ ሰውን በማክበር እንጂ ሰውን በማዋረድ ውስጥ የለችም።
የሚዲያ ተጠቃሚውም ቢሆን እንዲህ አይነት ሰብዓዊ ክብርን የሚጋፉ ይዘቶችን ከማበረታታት፣ ከማየት እና ከማጋራት በመቆጠብ ይህንን እኩይ ተግባር ሊያወግዘው ይገባል። ሰውን ማክበር ኋላቀርነት ሳይሆን የስልጣኔ ሁሉ ቁንጮ ነው።
በያፌት ገ/ህይወት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#ethiopia | የናቲ ገጠመኝ በግለሰብ ደረጃ የተፈጸመ ቅጥ አልባ ድርጊት ብቻ ሳይሆን በአሁኑ ወቅት በማህበራዊ ሚዲያ ላይ "እይታን" ለመቃረም ሲባል የሚደረግ የዘመኑ ልክፍት ነው።
ይህ ድርጊት ከቀልድነት አልፎ በሰዎች ሰላማዊ ህይወት ላይ የሚፈጸም ጥቃት ነው!
በመሠረቱ ፕራንክ የሚሉት ነገር ለዛ ቢስ ጨዋታ ነው ነገር ግን ፤ ይሁን ይደረግ ከተባለም (አድራጊውንም ሆነ ተደራጊውን) መጨረሻው የማያሳቅቅ እና የሰዎችን ስሜት የማይጎዳ መሆን ይገበዋል፤ አሁን አሁን ግን ሰዎችን ማዋከብ፣ ማስደንገጥ እና ስነ-ልቦናዊ ጫና ማድረስ እንደ መዝናኛ እየተቆጠረ ነው።
የናቲ ድንጋጤ እና ፊቱ ላይ ይነበብ የነበረው ጭንቀት ለነሱ "ጥሩ የቲክቶክ ቪዲዮ" ሲሆን፣ ለሱ ግን ትርጉሙ ሌላ ነው።
ሌላው የደንብ ልብስን አላግባብ መጠቀምስ ይቻላል ወይ?
አንደኛው ግለሰብ የፖሊስ ልብስ(የሚመስል) ለብሶ መምጣቱ ድርጊቱን ከስነ-ምግባር ግድፈት አልፎ ከባድ የህግ ጥሰት ያደርገዋል።
ዜጎች በጸጥታ አስከባሪዎች ላይ ሊኖራቸው የሚገባውን እምነት የሚሸረሽር እና የመንግስትን የደንብ ልብስ ለግል የሶሻል ሚዲያ ትርፍ ማዋረድ ነው።
የሰውን ልጅ ሰላም ነስቶ የሚገኝ ላይክ ዋጋው ስንት ነው?
መፍትሄው እና መማር ያለብን እሴት
፣ ከዚህ ሁሉ ጫጫታ እና የሰዎችን ክብር ከሚረግጥ አዝማሚያ ወጥተን ሰውን በማክበር ረገድ እንድናስብ ያስፈልጋል።
ጥበብ ሰውን በማክበር እንጂ ሰውን በማዋረድ ውስጥ የለችም።
የሚዲያ ተጠቃሚውም ቢሆን እንዲህ አይነት ሰብዓዊ ክብርን የሚጋፉ ይዘቶችን ከማበረታታት፣ ከማየት እና ከማጋራት በመቆጠብ ይህንን እኩይ ተግባር ሊያወግዘው ይገባል። ሰውን ማክበር ኋላቀርነት ሳይሆን የስልጣኔ ሁሉ ቁንጮ ነው።
በያፌት ገ/ህይወት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
6 days ago
የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ከኢንተርፖልና ከማላዊ ፖሊስ ጋር በመተባበር በአደገኛ ሕገ-ወጥ የሰዎች አዘዋዋሪነት ወንጀል የተጠረጠረውን አድነው ባሻው ውዳሞን በማላዊ በቁጥጥር ሥር በማዋል ወደ ኢትዮጵያ አምጥቷል።
ተጠርጣሪው ከግብረ አበሮቹ ጋር በመሆን በተለይም ከማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ከሀድያ እና ከንባታ ዞኖች በርካታ ወጣቶችን ሕይወታቸውን እንደሚያሻሽል በመሐላና በአጉል ተስፋ በማታለል ወደ ደቡብ አፍሪካ ሲያዘዋውር መቆየቱ በሰውና በሰነድ ማስረጃ ተረጋግጧል።
ተጓዦችን ከ600 ሺህ እስከ 800 ሺህ ብር ያስከፍል የነበረ ሲሆን፣ በቅድመ ክፍያ በኢትዮጵያ እስከ 100 ሺህ ብር እና ከዚያ በላይ በባንክ ይቀበል እንደነበር የምርመራ መዝገቡ ያመላክታል።
ተጓዦቹን በሞያሌ በኩል ወደ ኬንያ ካሻገረ በኋላ በጋንቦ ጫካ ውስጥ በድብቅ በማስቀመጥ በየ24 ሰዓቱ ትንሽ ሩዝ ከቁራጭ ዳቦ ጋር ብቻ በመስጠት ለከፍተኛ ረሃብና የውሃ ጥም የዳረጋቸው ሲሆን፣ በሞተርና በእግር ሴሎ በረሃን እንዲያቋርጡ አስገድዷቸዋል።
ናይሮቢ ካደረሳቸው በኋላም በአንድ ክፍል ውስጥ በማጎር ከቤተሰቦቻቸው ተጨማሪ ገንዘብ እንዲያስልኩ በማስገደድ፣ ገንዘብ ማስላክ ያልቻሉትን በዱላ በመደብደብና በኤሌክትሪክ ንዝረት በማሰቃየት ተጨማሪ ገንዘብ በኢትዮጵያ ባሉ ግብረ አበሮቹ በኩል እንዲከፈለው አድርጓል።
በተጨማሪም ተጓዦቹን ከናይሮቢ ወደ ሞምባሳና ታንዛኒያ በዕቃ መጫኛ ኮንቴነሮች፣ በተሳቢና በሸራ በተሸፈኑ መኪኖች ውስጥ አጉሮ በመጫን ታንዛኒያ በሚገኝ ጫካ ውስጥ ጥሏቸው የተሰወረ ሲሆን፣ አብዛኞቹ ወጣቶች ደቡብ አፍሪካ ሳይደርሱ በተለያዩ ሀገራት በፖሊስ ቁጥጥር ሥር ውለው እስከ ሦስት ዓመት እስራት ከተቀጡ በኋላ እስከ 170 ሺህ ብር ከፍለው ወደ ሀገር መመለሳቸው ተገልጿል።
ፌደራል ፖሊስ ከ2015 ዓ.ም ጀምሮ ባደረገው ክትትል ተጠርጣሪውን በማላዊ ፖሊስ አስይዞ ሐምሌ 22 ቀን 2018 ዓ.ም ተረክቦ ወደ ሀገር ያመጣው ሲሆን፣ ህብረተሰቡ በEFPApp፣ በ991 እና በSPS ጥቆማ በመስጠት ትብብሩን እንዲቀጥል ጥሪ አቅርቧል።
ተጠርጣሪው ከግብረ አበሮቹ ጋር በመሆን በተለይም ከማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ከሀድያ እና ከንባታ ዞኖች በርካታ ወጣቶችን ሕይወታቸውን እንደሚያሻሽል በመሐላና በአጉል ተስፋ በማታለል ወደ ደቡብ አፍሪካ ሲያዘዋውር መቆየቱ በሰውና በሰነድ ማስረጃ ተረጋግጧል።
ተጓዦችን ከ600 ሺህ እስከ 800 ሺህ ብር ያስከፍል የነበረ ሲሆን፣ በቅድመ ክፍያ በኢትዮጵያ እስከ 100 ሺህ ብር እና ከዚያ በላይ በባንክ ይቀበል እንደነበር የምርመራ መዝገቡ ያመላክታል።
ተጓዦቹን በሞያሌ በኩል ወደ ኬንያ ካሻገረ በኋላ በጋንቦ ጫካ ውስጥ በድብቅ በማስቀመጥ በየ24 ሰዓቱ ትንሽ ሩዝ ከቁራጭ ዳቦ ጋር ብቻ በመስጠት ለከፍተኛ ረሃብና የውሃ ጥም የዳረጋቸው ሲሆን፣ በሞተርና በእግር ሴሎ በረሃን እንዲያቋርጡ አስገድዷቸዋል።
ናይሮቢ ካደረሳቸው በኋላም በአንድ ክፍል ውስጥ በማጎር ከቤተሰቦቻቸው ተጨማሪ ገንዘብ እንዲያስልኩ በማስገደድ፣ ገንዘብ ማስላክ ያልቻሉትን በዱላ በመደብደብና በኤሌክትሪክ ንዝረት በማሰቃየት ተጨማሪ ገንዘብ በኢትዮጵያ ባሉ ግብረ አበሮቹ በኩል እንዲከፈለው አድርጓል።
በተጨማሪም ተጓዦቹን ከናይሮቢ ወደ ሞምባሳና ታንዛኒያ በዕቃ መጫኛ ኮንቴነሮች፣ በተሳቢና በሸራ በተሸፈኑ መኪኖች ውስጥ አጉሮ በመጫን ታንዛኒያ በሚገኝ ጫካ ውስጥ ጥሏቸው የተሰወረ ሲሆን፣ አብዛኞቹ ወጣቶች ደቡብ አፍሪካ ሳይደርሱ በተለያዩ ሀገራት በፖሊስ ቁጥጥር ሥር ውለው እስከ ሦስት ዓመት እስራት ከተቀጡ በኋላ እስከ 170 ሺህ ብር ከፍለው ወደ ሀገር መመለሳቸው ተገልጿል።
ፌደራል ፖሊስ ከ2015 ዓ.ም ጀምሮ ባደረገው ክትትል ተጠርጣሪውን በማላዊ ፖሊስ አስይዞ ሐምሌ 22 ቀን 2018 ዓ.ም ተረክቦ ወደ ሀገር ያመጣው ሲሆን፣ ህብረተሰቡ በEFPApp፣ በ991 እና በSPS ጥቆማ በመስጠት ትብብሩን እንዲቀጥል ጥሪ አቅርቧል።
6 days ago
የቀድሞው የኢንሳ ሲኒየር ሶፍትዌር ዴቨሎፐር በአሜሪካ በአሰቃቂ አደጋ ሕይወቱ ማለፉን ፖሊስ አስታወቀ። ዝርዝሩን በ5 ደቂቃ ውስጥ ይጠብቁ።
6 days ago
ወደ ስዊድን ያቀኑ 20 የእግርኳስ ቡድን አባላት መጥፋታቸው ተሰማ
ወደ ስዊድን ያቀኑ ዕድሜያቸው ከ 14 እስከ 17 የሚገመት 20 ታዳጊ የእግርኳስ ተጫዋቾች ከ መሪያቸው ጋር መጥፋታቸውን ስዊድን ሄራልድ ዘግቧል።
"ጎቲያካፕ" ለተሰኘ የእግር ኳስ ውድድር ከኢትዮጵያ የሔዱት ታዳጊዎች ካረፉበት ትምሕርት ቤት ሳያሳውቁ በመውጣት መሰወራቸውን የስዊድን ፖሊስ አስታውቋል።እግር ኳስ ተጫዋቾቹ ወደ ኢትዮጵያ እንዳልተመለሱ ያረጋገጠው ፖሊስ፤ በራሳቸው ፍላጎት ጠፍተው ሊሆን እንደሚችል አመላክቷል።
በጉዳዩ ዙርያ ምላሽ የሰጠው ፌደሬሽኑ የቡድኑ አባላት መጥፋት እንዳሳዘነው እና ታዳጊዎቹ በመሰል ውድድሮች ላይ በራሳቸው ጥረት በሚያገኙት እድል ወደ ውድድሩ ማምራታቸውን አሳውቋል።
በመሆኑም ታዳጊዎቹ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድንን የወከሉ አለመሆኑን እየገለፅን በአንዳንድ አካላት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን አባላት እንደሆኑ እየተገለጸበት ያለው መንገድ ትክክል አለመሆኑን እናሳውቃለን ብሏል ፌደሬሽንኑ።
ፖሊስ የጠፉት ታዳጊዎች ዕድሜያቸው ከ14 እስከ 17 ዓመት የሆኑ ወጣቶች ሲሆኑ፣ ከእነሱ ጋር አንድ ወይም ከዚያ በላይ የቡድን መሪዎች አብረው ጠፍተዋል ብሏል። ይህ የታወቀው በውድድሩ የመጨረሻ ቀን ሲሆን ያረፉበት ትምህርት ቤት አስተዳዳሪ አባላቱ ያለ ምንም ማስታወቂያ ለቀው መሄዳቸውን ካረጋገጠ በኋላ ለፖሊስ ማሳወቁም ተዘግቧል።
Seledadotio
Seledadotio
ወደ ስዊድን ያቀኑ ዕድሜያቸው ከ 14 እስከ 17 የሚገመት 20 ታዳጊ የእግርኳስ ተጫዋቾች ከ መሪያቸው ጋር መጥፋታቸውን ስዊድን ሄራልድ ዘግቧል።
"ጎቲያካፕ" ለተሰኘ የእግር ኳስ ውድድር ከኢትዮጵያ የሔዱት ታዳጊዎች ካረፉበት ትምሕርት ቤት ሳያሳውቁ በመውጣት መሰወራቸውን የስዊድን ፖሊስ አስታውቋል።እግር ኳስ ተጫዋቾቹ ወደ ኢትዮጵያ እንዳልተመለሱ ያረጋገጠው ፖሊስ፤ በራሳቸው ፍላጎት ጠፍተው ሊሆን እንደሚችል አመላክቷል።
በጉዳዩ ዙርያ ምላሽ የሰጠው ፌደሬሽኑ የቡድኑ አባላት መጥፋት እንዳሳዘነው እና ታዳጊዎቹ በመሰል ውድድሮች ላይ በራሳቸው ጥረት በሚያገኙት እድል ወደ ውድድሩ ማምራታቸውን አሳውቋል።
በመሆኑም ታዳጊዎቹ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድንን የወከሉ አለመሆኑን እየገለፅን በአንዳንድ አካላት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን አባላት እንደሆኑ እየተገለጸበት ያለው መንገድ ትክክል አለመሆኑን እናሳውቃለን ብሏል ፌደሬሽንኑ።
ፖሊስ የጠፉት ታዳጊዎች ዕድሜያቸው ከ14 እስከ 17 ዓመት የሆኑ ወጣቶች ሲሆኑ፣ ከእነሱ ጋር አንድ ወይም ከዚያ በላይ የቡድን መሪዎች አብረው ጠፍተዋል ብሏል። ይህ የታወቀው በውድድሩ የመጨረሻ ቀን ሲሆን ያረፉበት ትምህርት ቤት አስተዳዳሪ አባላቱ ያለ ምንም ማስታወቂያ ለቀው መሄዳቸውን ካረጋገጠ በኋላ ለፖሊስ ማሳወቁም ተዘግቧል።
Seledadotio
Seledadotio
6 days ago
በርካታ አካባቢዎች መብራት ይቋረጣል‼️
የጥገና ሥራ ምክንያት ነገ በበርካታ አካባቢዎች የመብራት አቅርቦት ይቋረጣል።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የጥገና ሥራ ለማከናወን ነገ ሐምሌ 23 ቀን 2018 ዓ.ም በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች የኃይል አቅርቦት ለተወሰነ ሰዓት እንደሚቋረጥ አስታውቋል።
ከጠዋቱ 4፡00 – 10፡00
• ኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት፣ ችሎት አደባባይ፣ ዘበኛ ሰፈር፣ ሾላ፣ ሰሜን ሆቴል ጫፍ፣ ቀለመወርቅ ት/ቤት፣ ዶሮ ተራ፣ ራስ ደስታ፣ አርበኞች ት/ቤት እና አካባቢያቸው።
• ዕንቁላል ፋብሪካ፣ ሀግቤስ አራት መንታ፣ ጎጃም በረንዳ፣ ጅንአድ፣ አበበች ጎበና፣ ቄጤማ ተራ፣ ፓስተር አደባባይ፣ አቤት ሆስፒታል፣ ቅዱስ ዮሐንስ ቤተክርስቲያን፣ ዳትሰን ሰፈር፣ ሰን ሆቴል እና አካባቢያቸው።
• 3ኛ ፖሊስ ጣቢያ፣ አዲስ አበባ ሜዲካል ኮሌጅ፣ ተክለሃይማኖት ቤተክርስቲያን፣ አትክልት ተራ፣ ጣሊያን ሰፈር፣ ፒያሳ (በከፊል)፣ ማዘጋጃ ቤት፣ አውቶብስ ተራ እና አካባቢያቸው።
• ማርቆስ መጋዘን፣ ቀጨኔ 8 ቁጥር ማዞሪያ፣ ቀጨኔ 1ኛ፣ 2ኛ እና 3ኛ መንገድ፣ ይመር ውኃ፣ መቀጠያ፣ 19 ታቦት ማደሪያ፣ መታፈሪ ሰፈር፣ ጴጥሮስ ሆስፒታል፣ ሽሮ ሜዳ እና አካባቢያቸው።
ከጠዋቱ 2፡00 – 10፡00
• አያት ለገጣፎ ሰብስቴሽን ፊትለፊት ያሉ ኮንዶሚኒየሞች፣ ክቡርደመና፣ ሰላም ቪሌጅ፣ ጣፎ ገብርኤል፣ ጋሪ ተራ፣ ባጃጅ ተራ እና አካባቢያቸው።
ከጠዋቱ 3፡00 – 10፡30
• ገላን፣ አራብሳ፣ እንጀራ ማምረቻ ፋብሪካ፣ ፕሮጀክት 13 አራብሳ ወታደር ሰፈር፣ ነጋ ቦንገር፣ ጀሶ ፋብሪካ፣ ብሔረፅጌ ቆዳ ፋብሪካ፣ ፓስታና መኮረኒ ፋብሪካ እና አካባቢያቸው።
• አባ ሳሙኤል፣ አቡሴራ፣ ሉግና፣ ዱፍና፣ ደበራ ጢኖ፣ ሻሸመኔ፣ ዱከም፣ በላይነህ ክንዴ፣ በስተቀኝ ያሉ ኢንዱስትሪዎች፣ ካፍ ማደያ እና አካባቢያቸው።
ከጠዋቱ 4፡30 – 11፡00
• መቐለ (ላቺ በከፊል)፣ ሀምዲያ ኢንዱስትሪ ዞን፣ ቀበሌ 03፣ ባህርዳር (አዲስ ዓለም)፣ ኦቪድ፣ ሰማኤታ፣ ሚሊኒየም ት/ቤት እና አካባቢያቸው።
ከጠዋቱ 1፡00 – 6፡00
• ወልዲያ፣ ይምርሃነ ክርስቶስ፣ ቢልባላ፣ ቂርቆስ፣ ሳሬዜና፣ ሶርባ፣ ላሊበላ፣ ገነተ ማርያም፣ ዘሃ፣ ሙቅ ውኃ፣ ተከዜ ገዳሜ፣ ኢርፋ ገለሶቴ እና አካባቢያቸው።
• ቅዱስ አርቢ፣ ዳቦ ከተማ፣ ቡርኮ፣ አይና ሚካኤል፣ ጭሮ፣ ሜኤሶ፣ አሰቦት እና አካባቢያቸው።
በመሆኑም በተጠቀሱት አካባቢዎች የምትገኙ ደንበኞች የጥገና ሥራው እስኪጠናቀቅ እና የኃይል አቅርቦቱ ወደ መደበኛ ሁኔታው እስኪመለስ ድረስ በትዕግስት እንዲጠብቁ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ጠይቋል።
Seledadotio
Seledadotio
የጥገና ሥራ ምክንያት ነገ በበርካታ አካባቢዎች የመብራት አቅርቦት ይቋረጣል።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የጥገና ሥራ ለማከናወን ነገ ሐምሌ 23 ቀን 2018 ዓ.ም በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች የኃይል አቅርቦት ለተወሰነ ሰዓት እንደሚቋረጥ አስታውቋል።
ከጠዋቱ 4፡00 – 10፡00
• ኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት፣ ችሎት አደባባይ፣ ዘበኛ ሰፈር፣ ሾላ፣ ሰሜን ሆቴል ጫፍ፣ ቀለመወርቅ ት/ቤት፣ ዶሮ ተራ፣ ራስ ደስታ፣ አርበኞች ት/ቤት እና አካባቢያቸው።
• ዕንቁላል ፋብሪካ፣ ሀግቤስ አራት መንታ፣ ጎጃም በረንዳ፣ ጅንአድ፣ አበበች ጎበና፣ ቄጤማ ተራ፣ ፓስተር አደባባይ፣ አቤት ሆስፒታል፣ ቅዱስ ዮሐንስ ቤተክርስቲያን፣ ዳትሰን ሰፈር፣ ሰን ሆቴል እና አካባቢያቸው።
• 3ኛ ፖሊስ ጣቢያ፣ አዲስ አበባ ሜዲካል ኮሌጅ፣ ተክለሃይማኖት ቤተክርስቲያን፣ አትክልት ተራ፣ ጣሊያን ሰፈር፣ ፒያሳ (በከፊል)፣ ማዘጋጃ ቤት፣ አውቶብስ ተራ እና አካባቢያቸው።
• ማርቆስ መጋዘን፣ ቀጨኔ 8 ቁጥር ማዞሪያ፣ ቀጨኔ 1ኛ፣ 2ኛ እና 3ኛ መንገድ፣ ይመር ውኃ፣ መቀጠያ፣ 19 ታቦት ማደሪያ፣ መታፈሪ ሰፈር፣ ጴጥሮስ ሆስፒታል፣ ሽሮ ሜዳ እና አካባቢያቸው።
ከጠዋቱ 2፡00 – 10፡00
• አያት ለገጣፎ ሰብስቴሽን ፊትለፊት ያሉ ኮንዶሚኒየሞች፣ ክቡርደመና፣ ሰላም ቪሌጅ፣ ጣፎ ገብርኤል፣ ጋሪ ተራ፣ ባጃጅ ተራ እና አካባቢያቸው።
ከጠዋቱ 3፡00 – 10፡30
• ገላን፣ አራብሳ፣ እንጀራ ማምረቻ ፋብሪካ፣ ፕሮጀክት 13 አራብሳ ወታደር ሰፈር፣ ነጋ ቦንገር፣ ጀሶ ፋብሪካ፣ ብሔረፅጌ ቆዳ ፋብሪካ፣ ፓስታና መኮረኒ ፋብሪካ እና አካባቢያቸው።
• አባ ሳሙኤል፣ አቡሴራ፣ ሉግና፣ ዱፍና፣ ደበራ ጢኖ፣ ሻሸመኔ፣ ዱከም፣ በላይነህ ክንዴ፣ በስተቀኝ ያሉ ኢንዱስትሪዎች፣ ካፍ ማደያ እና አካባቢያቸው።
ከጠዋቱ 4፡30 – 11፡00
• መቐለ (ላቺ በከፊል)፣ ሀምዲያ ኢንዱስትሪ ዞን፣ ቀበሌ 03፣ ባህርዳር (አዲስ ዓለም)፣ ኦቪድ፣ ሰማኤታ፣ ሚሊኒየም ት/ቤት እና አካባቢያቸው።
ከጠዋቱ 1፡00 – 6፡00
• ወልዲያ፣ ይምርሃነ ክርስቶስ፣ ቢልባላ፣ ቂርቆስ፣ ሳሬዜና፣ ሶርባ፣ ላሊበላ፣ ገነተ ማርያም፣ ዘሃ፣ ሙቅ ውኃ፣ ተከዜ ገዳሜ፣ ኢርፋ ገለሶቴ እና አካባቢያቸው።
• ቅዱስ አርቢ፣ ዳቦ ከተማ፣ ቡርኮ፣ አይና ሚካኤል፣ ጭሮ፣ ሜኤሶ፣ አሰቦት እና አካባቢያቸው።
በመሆኑም በተጠቀሱት አካባቢዎች የምትገኙ ደንበኞች የጥገና ሥራው እስኪጠናቀቅ እና የኃይል አቅርቦቱ ወደ መደበኛ ሁኔታው እስኪመለስ ድረስ በትዕግስት እንዲጠብቁ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ጠይቋል።
Seledadotio
Seledadotio
Sponsored by
Surafel
6 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) በስዊድን ጎተንበርግ ከተማ እየተካሄደ በሚገኘው የ'ጎቲያ ካፕ' የዓለም የወጣቶች እግር ኳስ ውድድር ላይ ለመሳተፍ ካቀኑት የኢትዮጵያ ቡድኖች መካከል፣ 20 የሚሆኑ የአንድ ቡድን ተጫዋቾች እና አጃቢ አዋቂዎች የውድድሩ ማጠቃለያ ዕለት ባልታሰበ ሁኔታ መሰወራቸው ተገልጿል። ይህ ክስተት በስፖርቱ ሽፋን በራሳቸው ፍቃድ የተፈጸመ ህገ-ወጥ ስደት (illegal migration) ሊሆን እንደሚችል የስዊድን ፖሊስ አስታውቋል።
ከ77 ሀገራት የተውጣጡ ቡድኖች በተሳተፉበት በዚህ ውድድር ኢትዮጵያ በአራት ቡድኖች ተወክላ ነበር። ሆኖም የፍጻሜው ውድድር በሚካሄድበት ዕለት የተጫዋቾቹ ማረፊያ የነበረው ትምህርት ቤት አስተናጋጆች፣ አባላቱ እቃቸውን ጠቅልለው መጥፋታቸውን ደርሰውበታል። የጎቲያ ካፕ የፕሬስ ቃል አቀባይ ፍሬድሪክ ቤክማን፣ አዘጋጁ ኮሚቴ ከቡድኑ ጋር ጥሩ ግንኙነት ስለነበረው ድርጊቱ እንዳስገረማቸው ገልጸው፣ ለጥንቃቄ ሲባል ለፖሊስ ሪፖርት ማድረጋቸውን ተናግረዋል። ውድድሩ ከተጠናቀቀ አስር ቀናት ቢያልፉም፣ የቡድኑ አባላት እስካሁን ወደ ኢትዮጵያ አልተመለሱም።
አዘጋጆቹ ከቡድኑ አስተባባሪ በደረሳቸው የኢሜል መልእክት "የተፈጠረው የመግባባት ችግር ነው" የሚል ማስተባበያ ቢሰጥም፣ ተጫዋቾቹ የት እንዳሉ ግን ምንም ዓይነት ፍንጭ አልተሰጠም። የስዊድን ፖሊስ የጠፉ ሰዎችን የመፈለግ ክፍል ኃላፊ ኤሊኖር ሃልዲን እንደገለጹት፣ ከዚህ በፊት በውድድሩ ታሪክ ጥቂት ሰዎች የመጥፋት አጋጣሚ ቢኖርም፣ በአንድ ጊዜ 20 ሰዎች ሲሰወሩ ግን ይህ የመጀመሪያው ነው።
ፖሊስ ከስደተኞች ኤጀንሲ እና ከድንበር ተቆጣጣሪዎች ጋር በመተባበር ፍለጋውን የቀጠለ ሲሆን፣ ድርጊቱ በሰው አዘዋዋሪዎች የተፈጸመ ሳይሆን አባላቱ አስቀድመው ያቀዱት ስደት መሆኑን መረጃዎች ያመለክታሉ።
ይህ ክስተት ዓለም አቀፍ ስፖርታዊ መድረኮች ላልተገባ የስደት ዓላማ መጠቀሚያ እየሆኑ መምጣታቸውን የሚያሳይ አሳሳቢ አጋጣሚ ሆኗል። ታዳጊ አትሌቶች እና አጃቢዎቻቸው ሀገራቸውን ወክለው በሄዱበት የውድድር መድረክ ላይ መሰወራቸው፣ በሀገራት መካከል ያለውን እምነት ከመፈተኑም በላይ፤ በቀጣይ ሌሎች ወጣት ኢትዮጵያውያን ስፖርተኞች ዓለም አቀፍ የውድድር ዕድሎችን እንዳያገኙ እና የቪዛ ክልከላ እንዲያጋጥማቸው ሊያደርግ የሚችል አደገኛ አዝማሚያ መሆኑ የጉዳዩን አሳሳቢነት ያጎላዋል።
የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ባወጣው መግለጫ፤ "ዓመታዊው የጎቲያ ካፕ ውድድር ላይ ለመካፈል ወደ ስዊድን ያመሩ ታዳጊዎች እና የቡድን አባላት በስዊድን መጥፋታቸውን አስመልክቶ የተለያዩ መረጃዎች እየወጡ ይገኛሉ። በጉዳዩ ዙርያ ምላሽ ወይም ማብራርያ እንድንሰጥ ወደ ኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ጥያቄዎች እየቀረቡ ሲሆን ፌዴሬሽናችን የቡድኑ አባላት መጥፋት ያሳዘነው መሆኑን እየገለጸ ታዳጊ ቡድኖች በመሰል ውድድሮች ላይ በራሳቸው ጥረት በሚያገኙት እድል ወደ ውድድሩ የሚያመሩ እንጂ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድንን የወከሉ አለመሆኑን እየገለፅን በአንዳድ አካላት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን አባላት እንደሆኑ እየተገለጸበት ያለው መንገድ ትክክል አለመሆኑን እናሳውቃለን። " ብሏል።
ከ77 ሀገራት የተውጣጡ ቡድኖች በተሳተፉበት በዚህ ውድድር ኢትዮጵያ በአራት ቡድኖች ተወክላ ነበር። ሆኖም የፍጻሜው ውድድር በሚካሄድበት ዕለት የተጫዋቾቹ ማረፊያ የነበረው ትምህርት ቤት አስተናጋጆች፣ አባላቱ እቃቸውን ጠቅልለው መጥፋታቸውን ደርሰውበታል። የጎቲያ ካፕ የፕሬስ ቃል አቀባይ ፍሬድሪክ ቤክማን፣ አዘጋጁ ኮሚቴ ከቡድኑ ጋር ጥሩ ግንኙነት ስለነበረው ድርጊቱ እንዳስገረማቸው ገልጸው፣ ለጥንቃቄ ሲባል ለፖሊስ ሪፖርት ማድረጋቸውን ተናግረዋል። ውድድሩ ከተጠናቀቀ አስር ቀናት ቢያልፉም፣ የቡድኑ አባላት እስካሁን ወደ ኢትዮጵያ አልተመለሱም።
አዘጋጆቹ ከቡድኑ አስተባባሪ በደረሳቸው የኢሜል መልእክት "የተፈጠረው የመግባባት ችግር ነው" የሚል ማስተባበያ ቢሰጥም፣ ተጫዋቾቹ የት እንዳሉ ግን ምንም ዓይነት ፍንጭ አልተሰጠም። የስዊድን ፖሊስ የጠፉ ሰዎችን የመፈለግ ክፍል ኃላፊ ኤሊኖር ሃልዲን እንደገለጹት፣ ከዚህ በፊት በውድድሩ ታሪክ ጥቂት ሰዎች የመጥፋት አጋጣሚ ቢኖርም፣ በአንድ ጊዜ 20 ሰዎች ሲሰወሩ ግን ይህ የመጀመሪያው ነው።
ፖሊስ ከስደተኞች ኤጀንሲ እና ከድንበር ተቆጣጣሪዎች ጋር በመተባበር ፍለጋውን የቀጠለ ሲሆን፣ ድርጊቱ በሰው አዘዋዋሪዎች የተፈጸመ ሳይሆን አባላቱ አስቀድመው ያቀዱት ስደት መሆኑን መረጃዎች ያመለክታሉ።
ይህ ክስተት ዓለም አቀፍ ስፖርታዊ መድረኮች ላልተገባ የስደት ዓላማ መጠቀሚያ እየሆኑ መምጣታቸውን የሚያሳይ አሳሳቢ አጋጣሚ ሆኗል። ታዳጊ አትሌቶች እና አጃቢዎቻቸው ሀገራቸውን ወክለው በሄዱበት የውድድር መድረክ ላይ መሰወራቸው፣ በሀገራት መካከል ያለውን እምነት ከመፈተኑም በላይ፤ በቀጣይ ሌሎች ወጣት ኢትዮጵያውያን ስፖርተኞች ዓለም አቀፍ የውድድር ዕድሎችን እንዳያገኙ እና የቪዛ ክልከላ እንዲያጋጥማቸው ሊያደርግ የሚችል አደገኛ አዝማሚያ መሆኑ የጉዳዩን አሳሳቢነት ያጎላዋል።
የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ባወጣው መግለጫ፤ "ዓመታዊው የጎቲያ ካፕ ውድድር ላይ ለመካፈል ወደ ስዊድን ያመሩ ታዳጊዎች እና የቡድን አባላት በስዊድን መጥፋታቸውን አስመልክቶ የተለያዩ መረጃዎች እየወጡ ይገኛሉ። በጉዳዩ ዙርያ ምላሽ ወይም ማብራርያ እንድንሰጥ ወደ ኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ጥያቄዎች እየቀረቡ ሲሆን ፌዴሬሽናችን የቡድኑ አባላት መጥፋት ያሳዘነው መሆኑን እየገለጸ ታዳጊ ቡድኖች በመሰል ውድድሮች ላይ በራሳቸው ጥረት በሚያገኙት እድል ወደ ውድድሩ የሚያመሩ እንጂ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድንን የወከሉ አለመሆኑን እየገለፅን በአንዳድ አካላት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን አባላት እንደሆኑ እየተገለጸበት ያለው መንገድ ትክክል አለመሆኑን እናሳውቃለን። " ብሏል።
6 days ago
በጎቲያ ካፕ የተሳተፉ 20 የሚጠጉ ኢትዮጵያውያን ታዳጊ ተጫዋቾችና የቡድን አመራሮች በስዊድን መሰወራቸው ተረጋገጠ
#ethiopia | በስዊድን ጎተንበርግ ከተማ በተካሄደው የ2026 የ«ጎቲያ ካፕ» ዓለም አቀፍ የታዳጊዎች እግር ኳስ ውድድር ላይ የተሳተፉ 20 የሚጠጉ ኢትዮጵያውያን ታዳጊ ተጫዋቾችና ቢያንስ አንድ የቡድን አመራር አባል ከውድድሩ በኋላ መሰወራቸውን የስዊድን ፖሊስ አረጋግጧል።
በስዊድን ፖሊስ መረጃ መሠረት፣ ቡድኑ ያረፈበትን ትምህርት ቤት ለቆ ያለማሳወቅ እንደወጣ ከታወቀ በኋላ ለፖሊስ ሪፖርት ተደርጓል። ፖሊስ እስካሁን የወንጀል፣ የሰው ዝውውር ወይም የግዳጅ ማስጠፋት ምልክት እንዳልተገኘ ገልጾ፣ ድርጊቱ በራሳቸው ፈቃድ የተፈጸመ እንደሚመስል አስታውቋል።
የጎቲያ ካፕ አዘጋጆች በበኩላቸው ከቡድኑ አንድ አመራር ጋር ግንኙነት እንዳደረጉ ገልጸው፣ ተጫዋቾቹ ከቤተሰቦቻቸው ጋር መገናኘታቸውንና በደህና መሆናቸውን ቢናገርም፣ አሁን የሚገኙበት ቦታ እንደማይታወቅ ገልጸዋል።
በኢትዮጵያ በኩል የእግር ኳስ ፌዴሬሽኑ የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ኃላፊ አቶ አብርሃም ገብረማሪያም፣ የተሰራጨው መረጃ እውነት መሆኑን አረጋግጠው፣ ወደ ስዊድን የሄደው ቡድን የኢትዮጵያን ብሔራዊ ቡድን ወክሎ የተላከ ሳይሆን በግል አደረጃጀት የተሰባሰበ ቡድን መሆኑን ገልጸዋል። በተጨማሪም ፌዴሬሽኑ በጉዳዩ ላይ ዝርዝር መግለጫ እንደሚያወጣ አስታውቋል።
«ጎቲያ ካፕ» በዓለም ላይ ትልቁ የታዳጊዎች የእግር ኳስ ውድድር ሲሆን፣ በ2026 ውድድሩ ከ78 አገራት የመጡ ከ45,000 በላይ ተጫዋቾችና አሰልጣኞች ተሳትፈዋል።
#ethiopia #gothiacup #sweden #sportsnews #getutemesgen #getunews
#ethiopia | በስዊድን ጎተንበርግ ከተማ በተካሄደው የ2026 የ«ጎቲያ ካፕ» ዓለም አቀፍ የታዳጊዎች እግር ኳስ ውድድር ላይ የተሳተፉ 20 የሚጠጉ ኢትዮጵያውያን ታዳጊ ተጫዋቾችና ቢያንስ አንድ የቡድን አመራር አባል ከውድድሩ በኋላ መሰወራቸውን የስዊድን ፖሊስ አረጋግጧል።
በስዊድን ፖሊስ መረጃ መሠረት፣ ቡድኑ ያረፈበትን ትምህርት ቤት ለቆ ያለማሳወቅ እንደወጣ ከታወቀ በኋላ ለፖሊስ ሪፖርት ተደርጓል። ፖሊስ እስካሁን የወንጀል፣ የሰው ዝውውር ወይም የግዳጅ ማስጠፋት ምልክት እንዳልተገኘ ገልጾ፣ ድርጊቱ በራሳቸው ፈቃድ የተፈጸመ እንደሚመስል አስታውቋል።
የጎቲያ ካፕ አዘጋጆች በበኩላቸው ከቡድኑ አንድ አመራር ጋር ግንኙነት እንዳደረጉ ገልጸው፣ ተጫዋቾቹ ከቤተሰቦቻቸው ጋር መገናኘታቸውንና በደህና መሆናቸውን ቢናገርም፣ አሁን የሚገኙበት ቦታ እንደማይታወቅ ገልጸዋል።
በኢትዮጵያ በኩል የእግር ኳስ ፌዴሬሽኑ የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ኃላፊ አቶ አብርሃም ገብረማሪያም፣ የተሰራጨው መረጃ እውነት መሆኑን አረጋግጠው፣ ወደ ስዊድን የሄደው ቡድን የኢትዮጵያን ብሔራዊ ቡድን ወክሎ የተላከ ሳይሆን በግል አደረጃጀት የተሰባሰበ ቡድን መሆኑን ገልጸዋል። በተጨማሪም ፌዴሬሽኑ በጉዳዩ ላይ ዝርዝር መግለጫ እንደሚያወጣ አስታውቋል።
«ጎቲያ ካፕ» በዓለም ላይ ትልቁ የታዳጊዎች የእግር ኳስ ውድድር ሲሆን፣ በ2026 ውድድሩ ከ78 አገራት የመጡ ከ45,000 በላይ ተጫዋቾችና አሰልጣኞች ተሳትፈዋል።
#ethiopia #gothiacup #sweden #sportsnews #getutemesgen #getunews
7 days ago
የጥገና ሥራ ለማከናወን የሚቋረጥ የኃይል አቅርቦት
ነገ ሐምሌ 23 ቀን 2018 ዓ.ም የጥገና ሥራ ለማከናወን የኃይል አቅርቦት የሚቋረጥባቸው አካባቢዎች፦
✅ከጠዋቱ 4፡00 – 10፡00
👉ኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት፣ ችሎት አደባባይ፣ዘበኛ ሰፈር፣ ሾላ፣ ሰሜን ሆቴል ጫፍ፣ ቀለመወርቅ ት/ቤት፣ ዶሮ ተራ፣ ራስ ደስታ አካባቢ፣ አርበኞች ት/ቤት እና አካባቢው፣
👉ዕንቁላል ፋብሪካ፣ ሀግቤስ አራት መንታ፣ ጎጃም በረንዳ ፣ ጅንአድ፣ አበበች ጎበና፣ ቄጤማ ተራ፣ ፓስተር አደባባይ፣ አቤት ሆስፒታል፣ ቅዱስ ዮሐንስ ቤ/ክ፣ ዳትሰን ሰፈር፣ ሰን ሆቴልእና አካባቢው ፣
👉3ኛ ፖሊስ ጣቢያ፣ አዲስ አበባ ሜዲካል ኮሌጅ፣ተ/ሃይማኖት ቤ/ክ፣ አትክልት ተራ፣ ጣሊያን ሰፈር፣ ፒያሳ በከፊል፣ ማዘጋጃ ቤት፣ አውቶብስ ተራ እና አካባቢው ፣
👉ማርቆስ መጋዘን ፣ ቀጨኔ 8 ቁጥር ማዞሪያ፣ ቀጨኔ 1ኛ፣2ኛ እና 3ኛ መንገድ ፣ ይመር ውኃ ፣ መቀጠያ፣ 19 ታቦት ማደሪያ፣ መታፈሪ ሰፈር፣ ጴጥሮስ ሆስፒታል፣ ሽሮ ሜዳ እና አካባቢው፣
✅ከጠዋቱ 2፡00 – 10፡00
👉አያት ለገጣፎ ሰብስቴሽን ፊትለፊት ያሉ ኮንዶሚኒየሞች፣ ክቡርደመና፣ ሰላም ቪሌጅ፣ ጣፎ ገብርኤል፣ ጋሪ ተራ፣ ባጃጅ ተራ እና አካባቢው፣
✅ከጠዋቱ 3፡00 – 10፡30
👉ገላን አካበቢ፣ አራብሳ፣ እንጀራ ማምረቻ ፋብሪካ፣ ፕሮጀክት 13 አራብሳ ወታደር ሰፈር፣ ነጋ ቦንገር ዝቅ ብሎ፣ ጀሶ ፋብሪካ፣ ብሔረፅጌ ቆዳ ፋብሪካ ፣ ፓስታና መኮረኒ እና አካባቢው፣
👉አባ ሳሙኤል፣ አቡሴራ፣ ሉግና ፣ ዱፍና፣ ደበራ ጢኖ፣ ሻሸመኔ፣ ዱከም፣በላይነህ ክንዴ፣ በስተቀኝ ያሉ ኢንዱስትሪዎች፣ ካፍ ማደያ እና አካባቢው ፣
✅ከጠዋቱ 4፡30 – 11፡00
👉መቐለ- መቐለ ላቺ በከፊል፣ ሀምዲያ ኢንዱስትሪ ዞን፣ ቀበሌ 03 ፣ ባህርዳር - አዲስ ዓለም፣ ኦቪድ፣ ሰማኤታ፣ሚሊኒየም ት/ቤት እና አካባቢው ፣
✅ከጠዋቱ 1፡00 – 6፡00
👉ወልዲያ - ይምርሃነ-ክርስቶስ፣ ቢልባላ፣ ቂርቆስ፣ ሳሬዜና፣ ሶርባ፣ ላሊይበላ ከተማ፣ ገነተማርያም፣ ዘሃ፣ ሙቅውኃ፣ ተከዜ ገዳሜ፣ ኢርፋ ገለሶቴ እና አካባቢው ፣
👉ቅዱስ አርቢ፣ ዳቦከተማ፣ ቡርኮ፣ አይና ሚኬል እና አካባቢው፣ጭሮ፣ ሜኤሶ፣ አሰቦት እና አካባቢው የኃይል አቅርቦት ተቋርጦ ይቆያል፡፡
ስለሆነም በተጠቀሱት አካባቢዎች የምትገኙ ክቡራን ደንበኞቻችን የጥገና ሥራው ተጠናቆ የኃይል አቅርቦቱ እስኪመለስ ድረስ በትዕግሰት እንድትጠብቁን እንጠይቃለን፡፡
#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት
ነገ ሐምሌ 23 ቀን 2018 ዓ.ም የጥገና ሥራ ለማከናወን የኃይል አቅርቦት የሚቋረጥባቸው አካባቢዎች፦
✅ከጠዋቱ 4፡00 – 10፡00
👉ኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት፣ ችሎት አደባባይ፣ዘበኛ ሰፈር፣ ሾላ፣ ሰሜን ሆቴል ጫፍ፣ ቀለመወርቅ ት/ቤት፣ ዶሮ ተራ፣ ራስ ደስታ አካባቢ፣ አርበኞች ት/ቤት እና አካባቢው፣
👉ዕንቁላል ፋብሪካ፣ ሀግቤስ አራት መንታ፣ ጎጃም በረንዳ ፣ ጅንአድ፣ አበበች ጎበና፣ ቄጤማ ተራ፣ ፓስተር አደባባይ፣ አቤት ሆስፒታል፣ ቅዱስ ዮሐንስ ቤ/ክ፣ ዳትሰን ሰፈር፣ ሰን ሆቴልእና አካባቢው ፣
👉3ኛ ፖሊስ ጣቢያ፣ አዲስ አበባ ሜዲካል ኮሌጅ፣ተ/ሃይማኖት ቤ/ክ፣ አትክልት ተራ፣ ጣሊያን ሰፈር፣ ፒያሳ በከፊል፣ ማዘጋጃ ቤት፣ አውቶብስ ተራ እና አካባቢው ፣
👉ማርቆስ መጋዘን ፣ ቀጨኔ 8 ቁጥር ማዞሪያ፣ ቀጨኔ 1ኛ፣2ኛ እና 3ኛ መንገድ ፣ ይመር ውኃ ፣ መቀጠያ፣ 19 ታቦት ማደሪያ፣ መታፈሪ ሰፈር፣ ጴጥሮስ ሆስፒታል፣ ሽሮ ሜዳ እና አካባቢው፣
✅ከጠዋቱ 2፡00 – 10፡00
👉አያት ለገጣፎ ሰብስቴሽን ፊትለፊት ያሉ ኮንዶሚኒየሞች፣ ክቡርደመና፣ ሰላም ቪሌጅ፣ ጣፎ ገብርኤል፣ ጋሪ ተራ፣ ባጃጅ ተራ እና አካባቢው፣
✅ከጠዋቱ 3፡00 – 10፡30
👉ገላን አካበቢ፣ አራብሳ፣ እንጀራ ማምረቻ ፋብሪካ፣ ፕሮጀክት 13 አራብሳ ወታደር ሰፈር፣ ነጋ ቦንገር ዝቅ ብሎ፣ ጀሶ ፋብሪካ፣ ብሔረፅጌ ቆዳ ፋብሪካ ፣ ፓስታና መኮረኒ እና አካባቢው፣
👉አባ ሳሙኤል፣ አቡሴራ፣ ሉግና ፣ ዱፍና፣ ደበራ ጢኖ፣ ሻሸመኔ፣ ዱከም፣በላይነህ ክንዴ፣ በስተቀኝ ያሉ ኢንዱስትሪዎች፣ ካፍ ማደያ እና አካባቢው ፣
✅ከጠዋቱ 4፡30 – 11፡00
👉መቐለ- መቐለ ላቺ በከፊል፣ ሀምዲያ ኢንዱስትሪ ዞን፣ ቀበሌ 03 ፣ ባህርዳር - አዲስ ዓለም፣ ኦቪድ፣ ሰማኤታ፣ሚሊኒየም ት/ቤት እና አካባቢው ፣
✅ከጠዋቱ 1፡00 – 6፡00
👉ወልዲያ - ይምርሃነ-ክርስቶስ፣ ቢልባላ፣ ቂርቆስ፣ ሳሬዜና፣ ሶርባ፣ ላሊይበላ ከተማ፣ ገነተማርያም፣ ዘሃ፣ ሙቅውኃ፣ ተከዜ ገዳሜ፣ ኢርፋ ገለሶቴ እና አካባቢው ፣
👉ቅዱስ አርቢ፣ ዳቦከተማ፣ ቡርኮ፣ አይና ሚኬል እና አካባቢው፣ጭሮ፣ ሜኤሶ፣ አሰቦት እና አካባቢው የኃይል አቅርቦት ተቋርጦ ይቆያል፡፡
ስለሆነም በተጠቀሱት አካባቢዎች የምትገኙ ክቡራን ደንበኞቻችን የጥገና ሥራው ተጠናቆ የኃይል አቅርቦቱ እስኪመለስ ድረስ በትዕግሰት እንድትጠብቁን እንጠይቃለን፡፡
#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት
7 days ago
በስዊድን የጎቲያ ካፕ ላይ የተሳተፉ 20 ያህል ኢትዮጵያውያን የቡድን አባላት መጥፋታቸው ተገለጸ
#fastmereja | በስዊድን ጎተንበርግ ከተማ በተካሄደው የጎቲያ ታዳጊዎች ውድድር (Gothia Cup) ላይ ለመሳተፍ የተጓዙ 20 ያህል ኢትዮጵያውያን ተጫዋቾች እና የቡድን መሪዎች ደብዛቸው መጥፋቱን የስዊድን ፖሊስ እና የውድድሩ አዘጋጆች አስታወቁ።
በየዓመቱ በስዊድን በሚካሄደው ዓለም አቀፍ የታዳጊዎች እግር ኳስ ውድድር ላይ ከተሳተፉ አራት የኢትዮጵያ ቡድኖች መካከል የአንዱ ቡድን አባላት የሆኑት እነዚህ 20 ያህል ግለሰቦች፣ ውድድሩ በተጠናቀቀበት የመጨረሻ ቀን ያረፉበት ትምህርት ቤት ሳይሰናበቱ መውጣታቸው ተሰምቷል። የቡድኑ አባላት እድሜያቸው ከ14 እስከ 17 ዓመት የሆኑ ታዳጊ ተጫዋቾችን እና ከአሰልጣኞች ወይም መሪዎች መካከል የተወሰኑትን ያካተተ መሆኑ ተመልክቷል።
የውድድሩ አዘጋጆች የቡድኑን መጥፋት እንደተረዱ ለአካባቢው ፖሊስ ጥቆማ ያቀረቡ ሲሆን፣ ቡድኑ ወደ ዋና ከተማዋ ስቶክሆልም አቅጣጫ ተጓዥ መሆናቸውን ጠቁመዋል። የስዊድን ፖሊስ ባደረገው ማጣራት እነዚህ ግለሰቦች ወደ ኢትዮጵያ እንዳልተመለሱ ያረጋገጠ ሲሆን፣ ክስተቱ በራሳቸው ፍላጎት የተደረገ መሰወር ወይም ህገ-ወጥ የፍልሰት እንቅስቃሴ እንደሆነ መገመቱን ገልጻል።
የስዊድን የምዕራብ ክልል ፖሊስ የጠፉ ሰዎች ክፍል ተወካይ ኤሊኖር ሃልዲን እንደገለጹት፣ በጉዳዩ ላይ የሰዎች ዝውውር ወይም የወንጀል ድርጊት መኖሩን የሚያሳይ ፍንጭ እስካሁን አልተገኘም። ሆኖም የስዊድን ፖሊስ ከአገሪቱ የኢሚግሬሽን መሥሪያ ቤት፣ ከድንበር ጠባቂዎች እና ከአለም አቀፍ አጋሮች ጋር በመተባበር የቡድኑን አባላት የመፈለግ ሥራ አጠናክሮ መቀጠሉን አስታውቋል።
#fastmereja | በስዊድን ጎተንበርግ ከተማ በተካሄደው የጎቲያ ታዳጊዎች ውድድር (Gothia Cup) ላይ ለመሳተፍ የተጓዙ 20 ያህል ኢትዮጵያውያን ተጫዋቾች እና የቡድን መሪዎች ደብዛቸው መጥፋቱን የስዊድን ፖሊስ እና የውድድሩ አዘጋጆች አስታወቁ።
በየዓመቱ በስዊድን በሚካሄደው ዓለም አቀፍ የታዳጊዎች እግር ኳስ ውድድር ላይ ከተሳተፉ አራት የኢትዮጵያ ቡድኖች መካከል የአንዱ ቡድን አባላት የሆኑት እነዚህ 20 ያህል ግለሰቦች፣ ውድድሩ በተጠናቀቀበት የመጨረሻ ቀን ያረፉበት ትምህርት ቤት ሳይሰናበቱ መውጣታቸው ተሰምቷል። የቡድኑ አባላት እድሜያቸው ከ14 እስከ 17 ዓመት የሆኑ ታዳጊ ተጫዋቾችን እና ከአሰልጣኞች ወይም መሪዎች መካከል የተወሰኑትን ያካተተ መሆኑ ተመልክቷል።
የውድድሩ አዘጋጆች የቡድኑን መጥፋት እንደተረዱ ለአካባቢው ፖሊስ ጥቆማ ያቀረቡ ሲሆን፣ ቡድኑ ወደ ዋና ከተማዋ ስቶክሆልም አቅጣጫ ተጓዥ መሆናቸውን ጠቁመዋል። የስዊድን ፖሊስ ባደረገው ማጣራት እነዚህ ግለሰቦች ወደ ኢትዮጵያ እንዳልተመለሱ ያረጋገጠ ሲሆን፣ ክስተቱ በራሳቸው ፍላጎት የተደረገ መሰወር ወይም ህገ-ወጥ የፍልሰት እንቅስቃሴ እንደሆነ መገመቱን ገልጻል።
የስዊድን የምዕራብ ክልል ፖሊስ የጠፉ ሰዎች ክፍል ተወካይ ኤሊኖር ሃልዲን እንደገለጹት፣ በጉዳዩ ላይ የሰዎች ዝውውር ወይም የወንጀል ድርጊት መኖሩን የሚያሳይ ፍንጭ እስካሁን አልተገኘም። ሆኖም የስዊድን ፖሊስ ከአገሪቱ የኢሚግሬሽን መሥሪያ ቤት፣ ከድንበር ጠባቂዎች እና ከአለም አቀፍ አጋሮች ጋር በመተባበር የቡድኑን አባላት የመፈለግ ሥራ አጠናክሮ መቀጠሉን አስታውቋል።
7 days ago
ከቁሉቢ ገብርኤል ንግስ ወደ ቤታቸው ሲመለሱ የነበሩ ሁለት የአንድ ቤተሰብ አባላት በትራፊክ አደጋ ህይወታቸው አለፈ
በኦሮሚያ ክልል አለልቱ አካባቢ በደረሰ አሳዛኝ የትራፊክ አደጋ ከቁሉቢ ገብርኤል ንግስ ወደ ቤታቸው ሲመለሱ የነበሩ ሁለት የአንድ ቤተሰብ አባላት ሕይወት ወዲያውኑ ማለፉ ተሰምቷል። የአሌልቱ ወረዳ ፖሊስ ፅህፈት ቤት አዛዥ ኢንስፔክተር መርድ ሙሉጌታ ለብስራት ሬዲዮ እንደተናገሩት ሐምሌ 21ቀን 2018 ከቀኑ ስምንት ሰዓት አደጋው ደርሷል።
በሠሜን ሸዋ ዞን አለሊቱ ወረዳ ጮሌ ቀበሌ ውስጥ፣ የሰሌዳ ቁጥሩ ኮድ 3-A-27185 ኢቲ
ጠጠር የጫነ ሲኖትራክ ከባድ ተሽከርካሪ ሌላ ተሽከርካሪ በመደረብ ለማለፍ ሲሞክር፣ ከሚኒባስ ተሽከርካሪ ጋር በመጋጨቱ ነው አደጋው ደርሷል።
በሚኒባስ ተሽከርካሪው ውስጥ ይጓዙ የነበሩት የደብረ ብርሐን ከተማ አጂፕ አካባቢ ነዋሪዎችና የአንድ ቤተሰብ አባላት ሲሆኑ፣ የቁሉቢ ገብርኤል ንግስ አንግሠው ወደ ቤታቸው ሲጓዙ አደጋው እንዳጋጠማቸው ገልፀዋል።በዚሁ አደጋ ወዲያው ሑለት ሴቶች ሲሞቱ ፣በሚኒባሱ ሹፌር ና ሁለት ህፃናት ላይ ከባድ ጉዳት በሌሎች አራት ሠዎች ላይ ደግሞ ቀላል አደጋ ስለደረሰበቸው በህክምና ላይ ይገኛሉ።
በአንዳንድ የማሕበራዊ ሚዲያ የሟቾች ቁጥር አራት ተብሎ ቢገለፅም እስካሑን ድረስ የደረሣቸው መረጃ እንደሌለ ኢንስፔክተር መርድ ሙሉጌታ ጨምረው ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል።
Seledadotio
Seledadotio
በኦሮሚያ ክልል አለልቱ አካባቢ በደረሰ አሳዛኝ የትራፊክ አደጋ ከቁሉቢ ገብርኤል ንግስ ወደ ቤታቸው ሲመለሱ የነበሩ ሁለት የአንድ ቤተሰብ አባላት ሕይወት ወዲያውኑ ማለፉ ተሰምቷል። የአሌልቱ ወረዳ ፖሊስ ፅህፈት ቤት አዛዥ ኢንስፔክተር መርድ ሙሉጌታ ለብስራት ሬዲዮ እንደተናገሩት ሐምሌ 21ቀን 2018 ከቀኑ ስምንት ሰዓት አደጋው ደርሷል።
በሠሜን ሸዋ ዞን አለሊቱ ወረዳ ጮሌ ቀበሌ ውስጥ፣ የሰሌዳ ቁጥሩ ኮድ 3-A-27185 ኢቲ
ጠጠር የጫነ ሲኖትራክ ከባድ ተሽከርካሪ ሌላ ተሽከርካሪ በመደረብ ለማለፍ ሲሞክር፣ ከሚኒባስ ተሽከርካሪ ጋር በመጋጨቱ ነው አደጋው ደርሷል።
በሚኒባስ ተሽከርካሪው ውስጥ ይጓዙ የነበሩት የደብረ ብርሐን ከተማ አጂፕ አካባቢ ነዋሪዎችና የአንድ ቤተሰብ አባላት ሲሆኑ፣ የቁሉቢ ገብርኤል ንግስ አንግሠው ወደ ቤታቸው ሲጓዙ አደጋው እንዳጋጠማቸው ገልፀዋል።በዚሁ አደጋ ወዲያው ሑለት ሴቶች ሲሞቱ ፣በሚኒባሱ ሹፌር ና ሁለት ህፃናት ላይ ከባድ ጉዳት በሌሎች አራት ሠዎች ላይ ደግሞ ቀላል አደጋ ስለደረሰበቸው በህክምና ላይ ይገኛሉ።
በአንዳንድ የማሕበራዊ ሚዲያ የሟቾች ቁጥር አራት ተብሎ ቢገለፅም እስካሑን ድረስ የደረሣቸው መረጃ እንደሌለ ኢንስፔክተር መርድ ሙሉጌታ ጨምረው ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል።
Seledadotio
Seledadotio
Sponsored by
Surafel
Comments